/// በእውቀቱ ስዩም//
አነጋገሬ የሰለጠነ
አረማመዴ የተመጠነ
ስደሰት ፊቴ :የግዚሀር ባውዛ
ስስም ከንፈሬ : ያበባ ጤዛ!!
ካለት ያወጋሁ
ከንብ የተጋሁ
እንደ ዘንገና : ውሃ የረጋሁ
ከጎህ ቀድሜ : ባይንሽ የነጋሁ::
ባስብ በመላ-ብናገር እውነት
ባቅፍሽ ክንዶቼ -የሃር መቀነት::
ጣትሽ ደባብሶኝ : ጥፍርሽ ቢበጣኝ
ዘቢብ ነው እንጂ :መች ደም ሊወጣኝ::
ለምድር ቢቀርብ- ቁመቴ ቢያጥር
በጎልያድ ግንባር- የማነጣጥር
ልቤ በጣቱ -ሰማይ ሚነካ
ከነራስ ደጀን- ከንጦጦ የካ
ቁመት በኩራት- የሚለካካ
ብትደገፊኝ -የላባ ፍራሽ
ብትመገቢኝ- የመና ቁራሽ::
እንኳን በጃኖ: እንኳን በሱፉ
እንደ ቁጥቋጦው : ልክ እንደዛፉ
ቅጠል ለብሼ :የምሽቀረቀር
የተለጋ ልብ: ቀልቤ ማስቀር
ያንቺው በረኛ
ያንቺው ቁንን ነኝ :ያንቺው ጉረኛ::
@getem
@getem
@gebriel_19
አነጋገሬ የሰለጠነ
አረማመዴ የተመጠነ
ስደሰት ፊቴ :የግዚሀር ባውዛ
ስስም ከንፈሬ : ያበባ ጤዛ!!
ካለት ያወጋሁ
ከንብ የተጋሁ
እንደ ዘንገና : ውሃ የረጋሁ
ከጎህ ቀድሜ : ባይንሽ የነጋሁ::
ባስብ በመላ-ብናገር እውነት
ባቅፍሽ ክንዶቼ -የሃር መቀነት::
ጣትሽ ደባብሶኝ : ጥፍርሽ ቢበጣኝ
ዘቢብ ነው እንጂ :መች ደም ሊወጣኝ::
ለምድር ቢቀርብ- ቁመቴ ቢያጥር
በጎልያድ ግንባር- የማነጣጥር
ልቤ በጣቱ -ሰማይ ሚነካ
ከነራስ ደጀን- ከንጦጦ የካ
ቁመት በኩራት- የሚለካካ
ብትደገፊኝ -የላባ ፍራሽ
ብትመገቢኝ- የመና ቁራሽ::
እንኳን በጃኖ: እንኳን በሱፉ
እንደ ቁጥቋጦው : ልክ እንደዛፉ
ቅጠል ለብሼ :የምሽቀረቀር
የተለጋ ልብ: ቀልቤ ማስቀር
ያንቺው በረኛ
ያንቺው ቁንን ነኝ :ያንቺው ጉረኛ::
@getem
@getem
@gebriel_19
አስር አረንጓዴ ጠርሙሶች
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ለሒሳብ ትምህርት...
መሰረት የጣሉ ፣ ተሰባሪ ቁሶች
የተዜመላቸው...
አስር አረንጓዴ ፣ መማሪያ ጠርሙሶች
ከትምህርት ቤቱ...
ካንዱ ግድግዳ ላይ ፣ እኩል ተደርድረው
መቀነስ ስንማር...
በተራ በተራ ፣ ያልቃሉ ተሰብረው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
"አስር አረንጓዴ ጠርሙሶች ፣ በግድድግዳ ላይ
ድንገት አንዱ መድቆ ቢሰበር ፣ ዘጠኝ ይቀራል
ዘጠኝ አረንጓዴ ጠርሙሶች ፣ በግድግዳ ላይ
ድንገት አንዱ ወድቆ ቢሰበር ፣ ስምንት ይቀራል.."
እንዲህ እንዲህ እያለ ፣ መምህሩ ያስተምራል
ለማስተማሪያ ስልት...
አስር አረንጓዴ ፣ ጠርሙስ ይሰበራል፡፡
በየ መማሪያው ቤት...
እንደ አስር ጠርሙስ ፣ ሆነው ሚቆጠሩ
በተማሪዎች ፊት ፣ ወድቀው ሚሰበሩ
ከቁጥር የበዙ...
ጠርሙሶች አውቃለሁ!
ካ'ስር ላይ ቀንሰው ፣ ዜሮ ላይ የቀሩ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
በየ መማሪያው ቤት....
ከቁጥር የበዛ ፣ የጠርሙስ ስባሪ
መስበር ማይሰለቸው ፣ ሒሳብ አስተማሪ
ለሚሰበር ጠርሙስ...
መዘመር የሚወድ ፣ ያልገባው ተማሪ
በሞላባት ሀገር
ጠርሙሱ ህይወቴ ፣ ካ'ሳብ ከቶኝ ነበር፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ሒሳቤን ከሀሳብ ፣ እየቀላቀልሁኝ
ሀሳቤን ከሒሳብ ፣ እያደባለቅሁኝ
ካ'ሳቤ ስነቃ ፣ መንገድ ላይ ነበርሁኝ
ሴተኛ አዳሪዎች...
ቆመው ይታዩኛል ፣ እኔ እየተማርሁኝ፡፡
እነዚህ አዳሪዎች...
አስር አረንጓዴ ፣ ጠርሙስ ይመስላሉ
አንዱ ወንድ ይመጣል...
አንዷን ይሰብራታል ፣ ዘጠኝ ይቀራሉ
አንዱ ወንድ ይመጣል...
አንዷን ይሰብራታል ፣ ስምንት ይቀራሉ
እንዲህ እንዲህ እያሉ...
ከማያቁት ገላ ፣ ወድቀው 'ሚሰበሩ
ካ'ስር ላይ ቀንሰው ፣ ዜሮ ላይ 'ሚቀሩ
እኔን ለማስተማር ፣ የሚሰበር ህይወት
ሰው ነው ጠርሙስ ማለት!!!
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እናም እኛ ሰዎች...
ነገ ተረኞች ነን ፣ ወድቀን ምንሰበር
ካ.ስር ላይ ቀንሰን ፣ ዜሮ ላይ የምንቀር፡፡
ዜሮነት ህይወት ላይ...
እልፍ ህይወት ቢባዛ ፣ እልፍ ቢጨመርም
ምላሹ ዜሮ ነው!!!
በመቀነስ ስሌት ፣ ለውጥ አይፈጠርም
ምክንያቱ ደሞ...
ዜሮ አይባዛም ፣ ዜሮ አይካፈልም፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ለውጥ ላለመፍጠር ...
የሚቀነስ ህይወት ፣ የሚሰበር አካል
ያልገባው ተማሪ ፣ ሲዘምር ይረካል፡፡
"አስር አረንጓዴ ጠርሙሶች ፣ በግድግዳ ላይ
ድንገት አንዱ ወድቆ ቢሰበር ፣ ዘጠኝ ይቀራል
ዘጠኝ አረንጓዴ ጠርሙሶች ፣ በግድግዳ ላይ
ድንገት አንዱ ወድቆ ቢሰበር ፣ ስምንት ይቀራል..."
እንዲህ እንዲህ እያለ ፣ መምህሩ ያስተምራል
ለማስተማሪያ ስልት...
አስር አረንጓዴ ፣ ጠርሙስ ይሰበራል፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
በየ መማሪያው ቤት...
ከቁጥር የበዛ ፣ የጠርሙስ ስባሪ
መስበር ማይሰለቸው ፣ ሒሳብ አስተማሪ
ለሚሰበር ጠርሙስ...
መዘመር የሚወድ ፣ ያልገባው ተማሪ
...........................እንዲገባው ሲባል...
ጠርሙስ ህይወት ሁሉ ፣
"ከሒሳብ ስሌት ውስጥ...
የመቀነስ ስሌት ፣ ሊቀነስ ይገባል"
እያለ ያስባል!!!
@getem
@getem
@gebriel_19
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ለሒሳብ ትምህርት...
መሰረት የጣሉ ፣ ተሰባሪ ቁሶች
የተዜመላቸው...
አስር አረንጓዴ ፣ መማሪያ ጠርሙሶች
ከትምህርት ቤቱ...
ካንዱ ግድግዳ ላይ ፣ እኩል ተደርድረው
መቀነስ ስንማር...
በተራ በተራ ፣ ያልቃሉ ተሰብረው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
"አስር አረንጓዴ ጠርሙሶች ፣ በግድድግዳ ላይ
ድንገት አንዱ መድቆ ቢሰበር ፣ ዘጠኝ ይቀራል
ዘጠኝ አረንጓዴ ጠርሙሶች ፣ በግድግዳ ላይ
ድንገት አንዱ ወድቆ ቢሰበር ፣ ስምንት ይቀራል.."
እንዲህ እንዲህ እያለ ፣ መምህሩ ያስተምራል
ለማስተማሪያ ስልት...
አስር አረንጓዴ ፣ ጠርሙስ ይሰበራል፡፡
በየ መማሪያው ቤት...
እንደ አስር ጠርሙስ ፣ ሆነው ሚቆጠሩ
በተማሪዎች ፊት ፣ ወድቀው ሚሰበሩ
ከቁጥር የበዙ...
ጠርሙሶች አውቃለሁ!
ካ'ስር ላይ ቀንሰው ፣ ዜሮ ላይ የቀሩ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
በየ መማሪያው ቤት....
ከቁጥር የበዛ ፣ የጠርሙስ ስባሪ
መስበር ማይሰለቸው ፣ ሒሳብ አስተማሪ
ለሚሰበር ጠርሙስ...
መዘመር የሚወድ ፣ ያልገባው ተማሪ
በሞላባት ሀገር
ጠርሙሱ ህይወቴ ፣ ካ'ሳብ ከቶኝ ነበር፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ሒሳቤን ከሀሳብ ፣ እየቀላቀልሁኝ
ሀሳቤን ከሒሳብ ፣ እያደባለቅሁኝ
ካ'ሳቤ ስነቃ ፣ መንገድ ላይ ነበርሁኝ
ሴተኛ አዳሪዎች...
ቆመው ይታዩኛል ፣ እኔ እየተማርሁኝ፡፡
እነዚህ አዳሪዎች...
አስር አረንጓዴ ፣ ጠርሙስ ይመስላሉ
አንዱ ወንድ ይመጣል...
አንዷን ይሰብራታል ፣ ዘጠኝ ይቀራሉ
አንዱ ወንድ ይመጣል...
አንዷን ይሰብራታል ፣ ስምንት ይቀራሉ
እንዲህ እንዲህ እያሉ...
ከማያቁት ገላ ፣ ወድቀው 'ሚሰበሩ
ካ'ስር ላይ ቀንሰው ፣ ዜሮ ላይ 'ሚቀሩ
እኔን ለማስተማር ፣ የሚሰበር ህይወት
ሰው ነው ጠርሙስ ማለት!!!
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እናም እኛ ሰዎች...
ነገ ተረኞች ነን ፣ ወድቀን ምንሰበር
ካ.ስር ላይ ቀንሰን ፣ ዜሮ ላይ የምንቀር፡፡
ዜሮነት ህይወት ላይ...
እልፍ ህይወት ቢባዛ ፣ እልፍ ቢጨመርም
ምላሹ ዜሮ ነው!!!
በመቀነስ ስሌት ፣ ለውጥ አይፈጠርም
ምክንያቱ ደሞ...
ዜሮ አይባዛም ፣ ዜሮ አይካፈልም፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ለውጥ ላለመፍጠር ...
የሚቀነስ ህይወት ፣ የሚሰበር አካል
ያልገባው ተማሪ ፣ ሲዘምር ይረካል፡፡
"አስር አረንጓዴ ጠርሙሶች ፣ በግድግዳ ላይ
ድንገት አንዱ ወድቆ ቢሰበር ፣ ዘጠኝ ይቀራል
ዘጠኝ አረንጓዴ ጠርሙሶች ፣ በግድግዳ ላይ
ድንገት አንዱ ወድቆ ቢሰበር ፣ ስምንት ይቀራል..."
እንዲህ እንዲህ እያለ ፣ መምህሩ ያስተምራል
ለማስተማሪያ ስልት...
አስር አረንጓዴ ፣ ጠርሙስ ይሰበራል፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
በየ መማሪያው ቤት...
ከቁጥር የበዛ ፣ የጠርሙስ ስባሪ
መስበር ማይሰለቸው ፣ ሒሳብ አስተማሪ
ለሚሰበር ጠርሙስ...
መዘመር የሚወድ ፣ ያልገባው ተማሪ
...........................እንዲገባው ሲባል...
ጠርሙስ ህይወት ሁሉ ፣
"ከሒሳብ ስሌት ውስጥ...
የመቀነስ ስሌት ፣ ሊቀነስ ይገባል"
እያለ ያስባል!!!
@getem
@getem
@gebriel_19
የፍቅር ሚዛን
ማነው ያቀለለው ፍቅርን እንደዋዛ
ማረፊያ ሲሆነን ለልባችን ታዛ
እንቧይ አልነበረም የፍቅራችን ካቡ
መፅናት የተሳነው ሚናድ በቀላሉ
እንዲህ አልነበረም የኔና ያንቺ ወጉ
ፍቅራችንም ሀያል የመዋደድ ጥጉ
የይስሙላ ያይደል ወረትም ያልቃኘው
ራስ ወዳድነት ቀርቦ ያልጎበኘው
እልፍ ቀኖች አሉ እኛን የሚወቅሱ
በግርምታ አፍዘው ትዝታን 'ሚጠቅሱ
እልፍ ቀኖች አሉ ያለፉ 'ሚመስሉ
ከልባችን መዝገብ ሊፋቁ 'ማይችሉ
ከ'ኔጋ ከ'ንቺ ጋር ዛሬም ድረስ ያሉ
ትላንት
አትለያየን ብሎ ሲማልድ የኖረ
ዛሬ
ጥዋቱን ተነስቶ አለያየን ብሎ ግብር ከገበረ
ለፍቅር አፀፋ ጥላቻ ካኖረ
ውህደት አፍርሶ ብቻውን ካበረ
አያሳቡ አሳቦ በሰበብ ተስቦ
ሸኙኝ ልሂድ ካለ
ታዲያ ምን ታከተ???
አያስቀሩት ነገር ልብም ከሸፈተ
ብቻ.......
በፍቅር ሚዛን ላይ ፍቅር ያመዝናል
እንከን አልባ ሆኖ ሚዛኑን ይደፋል
ጥላቻ ግን ሲሆን ፍቅርን ያጎድላል
ስህተትን ያጎላል
እናም....
ፍፅምና አይደለም የኔ መመዘኛ
ሚዛኔ ፍቅር ነው አይደል የጥላቻ
መኖርን ብትመርጪም ከ'ራስሽ ጋር ብቻ
እኔስ 'ወድሻለው ያለአቻ ለብቻ!!
ጌትነት አብይ 9/6/11
@getem
@getem
@gebriel_19
ማነው ያቀለለው ፍቅርን እንደዋዛ
ማረፊያ ሲሆነን ለልባችን ታዛ
እንቧይ አልነበረም የፍቅራችን ካቡ
መፅናት የተሳነው ሚናድ በቀላሉ
እንዲህ አልነበረም የኔና ያንቺ ወጉ
ፍቅራችንም ሀያል የመዋደድ ጥጉ
የይስሙላ ያይደል ወረትም ያልቃኘው
ራስ ወዳድነት ቀርቦ ያልጎበኘው
እልፍ ቀኖች አሉ እኛን የሚወቅሱ
በግርምታ አፍዘው ትዝታን 'ሚጠቅሱ
እልፍ ቀኖች አሉ ያለፉ 'ሚመስሉ
ከልባችን መዝገብ ሊፋቁ 'ማይችሉ
ከ'ኔጋ ከ'ንቺ ጋር ዛሬም ድረስ ያሉ
ትላንት
አትለያየን ብሎ ሲማልድ የኖረ
ዛሬ
ጥዋቱን ተነስቶ አለያየን ብሎ ግብር ከገበረ
ለፍቅር አፀፋ ጥላቻ ካኖረ
ውህደት አፍርሶ ብቻውን ካበረ
አያሳቡ አሳቦ በሰበብ ተስቦ
ሸኙኝ ልሂድ ካለ
ታዲያ ምን ታከተ???
አያስቀሩት ነገር ልብም ከሸፈተ
ብቻ.......
በፍቅር ሚዛን ላይ ፍቅር ያመዝናል
እንከን አልባ ሆኖ ሚዛኑን ይደፋል
ጥላቻ ግን ሲሆን ፍቅርን ያጎድላል
ስህተትን ያጎላል
እናም....
ፍፅምና አይደለም የኔ መመዘኛ
ሚዛኔ ፍቅር ነው አይደል የጥላቻ
መኖርን ብትመርጪም ከ'ራስሽ ጋር ብቻ
እኔስ 'ወድሻለው ያለአቻ ለብቻ!!
ጌትነት አብይ 9/6/11
@getem
@getem
@gebriel_19
እኔው ነኝ አህያዋ
'""""""""""""""""""
ለትልቅ ክብር ታጭቼ
የዋልኩ ከክብር ቦታ
ጌታዬን ተሸክሜ
በዘንባባ በሰው ሆታ
በአጀባ .........በእልልታ!!!
ጌታዬን በላዬ አኑሬ
ዘንባባውን እየረገጥኩ እንዳልተባለ እልል እልል
እኔው ነኝ አህያዋ...
በማግስቱ በመጫኛ የሸከሙኝ ኩንታል እህል
(እኔው ነኝ አህያዋ)
ተሸክሜ የተመታሁ እየተባልኩኝ ገጣባ
አለዳዬ የምሸከም ዘላለሙን የማነባ
የተቆጠርኩ ከማልረባ
(እኔው ነኝ ...አህያዋ)
በገዛ እጄ ከከፍታው
አለመጠን ያልኩኝ ወረድ
ክብር ያላት እኔነቴን
ያስቆጠርኳት እንደ ገረድ
ዘላለሙን የምዋረድ
ዘላለሙን የምዋትት
እኔው ነኝ አህያዋ
አያ ሞኚት.....አያ ጅልዋ
አመድ አፋሽ ተቀጪዋ
ተመቺዋ.....ተገፊዋ
ችሎ ማደር....ታጋሽ ልብዋ
እኔው ነኝ አህያዋ
✍አብርሃም
(😔😔😔)
@getem
@getem
@gebriel_19
'""""""""""""""""""
ለትልቅ ክብር ታጭቼ
የዋልኩ ከክብር ቦታ
ጌታዬን ተሸክሜ
በዘንባባ በሰው ሆታ
በአጀባ .........በእልልታ!!!
ጌታዬን በላዬ አኑሬ
ዘንባባውን እየረገጥኩ እንዳልተባለ እልል እልል
እኔው ነኝ አህያዋ...
በማግስቱ በመጫኛ የሸከሙኝ ኩንታል እህል
(እኔው ነኝ አህያዋ)
ተሸክሜ የተመታሁ እየተባልኩኝ ገጣባ
አለዳዬ የምሸከም ዘላለሙን የማነባ
የተቆጠርኩ ከማልረባ
(እኔው ነኝ ...አህያዋ)
በገዛ እጄ ከከፍታው
አለመጠን ያልኩኝ ወረድ
ክብር ያላት እኔነቴን
ያስቆጠርኳት እንደ ገረድ
ዘላለሙን የምዋረድ
ዘላለሙን የምዋትት
እኔው ነኝ አህያዋ
አያ ሞኚት.....አያ ጅልዋ
አመድ አፋሽ ተቀጪዋ
ተመቺዋ.....ተገፊዋ
ችሎ ማደር....ታጋሽ ልብዋ
እኔው ነኝ አህያዋ
✍አብርሃም
(😔😔😔)
@getem
@getem
@gebriel_19
የባረቀ ፍቅር
(ረድኤት አሰፋ)
.
ሴባስቶፖል ልቤ~በሚያሳብድ ፍቅር ~የተቀጠቀጠ
ከሚስጥር ጋራዬ~ለልብሽ ሊተኮስ~እንዳልተቀመጠ
.
.
ንፍገትሽ ቢደፍነው~ከንፈሬ ታጠፈ
ባጣመምሽው አፌ.~ጥያቄው ከሸፈ
ላንቺ የታለመው~የፍቅሬ ኢላማ~ለራሴው ተረፈ
.
.
.
ራሴን ወደድኩት .... !
ራሴን ገደልኩት .... !
.
"እኔ" "ያለኔ" "አልኖር " በተባለ ጥይት !
.
.
የከበበኝ ስምሽ~ከሃሜት በስተቀር.~እዉነቱን አፈነ
በ'የርሱ' ናት ተስፋ.~የፈላጊዮቼ~ጥያቄ መከነ
.
.
ካንድ ሽጉጥና~ከሶስት ጥይት በቀር~አልተረፈም በጄ
መድፌም ወደኔው ነው~ላንቺ አልወድረውም~ራሴን ወድጄ !
.
.
አንድ ሽጉጥና~ሶስት ጥይት ብቻ
"ብትኖርስ" የምለው~የለኝም ፍራቻ
.
የሶስት ጥይት ቋንቋ
"እኔ " "ያላንቺ " " አልኖርም" እሞታለሁ በቃ
.
ሊያዉም በኛ ዘመን~ሞት ዋጋው ተወዶ~እየተናፈቀ
ሳልሰስት ልሠጥሽ~የቀዳሁት ፅዋ~በንቀትሽ ታጥፎ~ካፌ ተጣበቀ
የተኮስኩት ፍቅሬ~ለራሴው ባረቀ
.
.
ራሴን ወደድኩት
ራሴን ገደልኩት
.
.
.
ሞት በናፈቀ ፊት~ቆመሻል ከፊቴ
ሽጉጤ አንድ ነው~ሶስት ናት ጥይቴ
.
.
.
ከመድፌ ትናጋ~የተኮስኩት ጥይት~ተራራ ላይ ባክኗል
ግን ልቤ ደግ ነው.~ለራሱ ካኖረው~ሶስት ፍሬ ጥይት~ሶስቱን ላንቺ
አጭቷል
.
.
የመድፌ ኢላማ~በንፍገትሽ ዞሮ~ከሽፎ ቢመለስም
ለሳሳች ተስፋዬ~መክደኛ ያልኩትን~ሶስት ጥይት አልሻም
ይኸው አንቺ ሙቺ~ "እኔ" "ያላንቺ" "አልኖርም "
"ድም" ~ "ድም " ~ "ድም"
.
@getem
@getem
@gebriel_19
(ረድኤት አሰፋ)
.
ሴባስቶፖል ልቤ~በሚያሳብድ ፍቅር ~የተቀጠቀጠ
ከሚስጥር ጋራዬ~ለልብሽ ሊተኮስ~እንዳልተቀመጠ
.
.
ንፍገትሽ ቢደፍነው~ከንፈሬ ታጠፈ
ባጣመምሽው አፌ.~ጥያቄው ከሸፈ
ላንቺ የታለመው~የፍቅሬ ኢላማ~ለራሴው ተረፈ
.
.
.
ራሴን ወደድኩት .... !
ራሴን ገደልኩት .... !
.
"እኔ" "ያለኔ" "አልኖር " በተባለ ጥይት !
.
.
የከበበኝ ስምሽ~ከሃሜት በስተቀር.~እዉነቱን አፈነ
በ'የርሱ' ናት ተስፋ.~የፈላጊዮቼ~ጥያቄ መከነ
.
.
ካንድ ሽጉጥና~ከሶስት ጥይት በቀር~አልተረፈም በጄ
መድፌም ወደኔው ነው~ላንቺ አልወድረውም~ራሴን ወድጄ !
.
.
አንድ ሽጉጥና~ሶስት ጥይት ብቻ
"ብትኖርስ" የምለው~የለኝም ፍራቻ
.
የሶስት ጥይት ቋንቋ
"እኔ " "ያላንቺ " " አልኖርም" እሞታለሁ በቃ
.
ሊያዉም በኛ ዘመን~ሞት ዋጋው ተወዶ~እየተናፈቀ
ሳልሰስት ልሠጥሽ~የቀዳሁት ፅዋ~በንቀትሽ ታጥፎ~ካፌ ተጣበቀ
የተኮስኩት ፍቅሬ~ለራሴው ባረቀ
.
.
ራሴን ወደድኩት
ራሴን ገደልኩት
.
.
.
ሞት በናፈቀ ፊት~ቆመሻል ከፊቴ
ሽጉጤ አንድ ነው~ሶስት ናት ጥይቴ
.
.
.
ከመድፌ ትናጋ~የተኮስኩት ጥይት~ተራራ ላይ ባክኗል
ግን ልቤ ደግ ነው.~ለራሱ ካኖረው~ሶስት ፍሬ ጥይት~ሶስቱን ላንቺ
አጭቷል
.
.
የመድፌ ኢላማ~በንፍገትሽ ዞሮ~ከሽፎ ቢመለስም
ለሳሳች ተስፋዬ~መክደኛ ያልኩትን~ሶስት ጥይት አልሻም
ይኸው አንቺ ሙቺ~ "እኔ" "ያላንቺ" "አልኖርም "
"ድም" ~ "ድም " ~ "ድም"
.
@getem
@getem
@gebriel_19
ፍቅር ፈራን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነትን ለመድን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
"ናቅን"
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
"ናቅን"
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
"ጠላን"
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
"ራቅን"
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን
©ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
@getem
@getem
@gebriel_19
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነትን ለመድን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
"ናቅን"
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
"ናቅን"
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
"ጠላን"
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
"ራቅን"
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን
©ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
@getem
@getem
@gebriel_19
ከወዳደቁ ነገሮች የተሠራ ሕይወት 2
(ያዴል ትዕዛዙ)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አሮጌ መሰንቆ
ሕይወት የገፋቸው ግጥም ሰጭ ጠጪዎች
ተቀምጠው ማያውቁ ቋሚ አዝማሪዎች
እና ደግሞ ተራ
የመንገድ ኩታራ...
እነኚህ ባሉበት
ግጥም ሰቆቃ ነው አሳር ሚበሉበት።
፣
ጠጪ አንድ
"ተቀበል አዝማሪ
መግፋት ቢከብደኝም
የእንጀራዬን ወፍጮ የሕይወቴን መጅ
እድሜ ለስካሬ
በተስፋ እኖራለሁ እየጠጣሁ ጠጅ።
እግዜር ይረሳኛል አይልም ድሀ አምልጦት
እምነቱን ይገምዳል ይፈትላል በእጦት።
ብቻ በቀደም ለት
እንዲህ እንደዛሬው መጠጫ አቶ ኪሴ
ቤት በጊዜ ገባሁ
ጨብጠው አገኘሁ
ሴት ልጄ ባሕር ዛፍ ሚስቴ ዳማ ከሴ።"
፣
ሕይወት አንድ የተሰራበት ቁስ አካል እና አዘገጃጀቱ
ነጭ ባሕር ዛፍ!
(ልክ እንደስሙና ልክ እንደታሪኩ
የባሕር ዛፍ ነገር ሁለት ነው መልኩ!)
ሳል ያሰቃየን ቀን
ይህን ነጭ ባህር ዛፍ መንደሬው ቀቅሎ
ፈውስ ነው ይለዋል
ሳምባህን አፍኖ "ጉነፋኑን ነቃቅሎ።"
ደግሞ እንደሰማነው
ባህር ዛፍ ተፈጥሮው ባህር ዛፍ አመሉ
የምድርን ሆድ መጦ
ለራሱ ሲፋፋ ሌላውን እፅዋት እድገት መከልከሉ።
፣
መንገድ ላይ የቀረ ምስኪንዬ ህጣን
መንገድ ዳር ተቀምጦ
ጠጅ ቤቱን እያየ
የግጥሙን አስኳል በመተርጎም ቀጣን።
"በየብርዱ ግንባር
ተሰጥቼ ምኖር
እኔ የዓለም ቅዳጅ የቀዬው እራፊ
ከቀን ጣቃ መሃል
ሳይመትሩ ቀደው
ቧጭሮኝ የምባክን የቀን ሽርፍራፊ
መኖርና ነፋስ
ነፍስያዬን ጨንቋት
ሳል እያጣደፈኝ ለጩኸት ባልበቃም
ፈውስ ነው አትበሉኝ
ስም በማቀያየር ሕይወት አይጠረቃም።
፣
እንደየባሕሩ እንደየዛፉ አቅም
ከደረቅ መሬት ላይ ፈውስ ስንለቅም
ሁለትዜ ሳትን
አንዴም ባሕር ዛፉን
ባሕር በሌለበት የብስ ላይ ስንተክለው
አንዴም ፈውስ ሽተን
ውኃችንን ግተን በ‘ሳት ስንቀቅለው።
እንዲህ ነው ልጅ መሆን እያደሩ ማነስ
ዳማ ከሴው ሲሻር
ባንዱ ነጩን ይዞ
በየተገኘው ላይ ጥውለጋን መነስነስ።
በየደረሱበት ኅልፈትን ማነፍነፍ
ስም እየቀየሩ ሁለቴ መሸነፍ።
እኔ ያለም ቅዳጅ
የቀዬው እራፊ
የዶፍ ብርዱ ወዳጅ
የሰው ትርፍራፊ
መጥቀሚያ መርፌና ክሬን አንጠልጥዬ
"እሰፋለሁ" ስል ነው የቀረሁ ተጥዬ።"
፣
ጠጪ ሁለት
"ተቀበል አዝማሪ
ምነው ይሄ ጎጆ
ምን ጠቢብ ቢያንፀው
ለመዳመን ሰፋ ማባራት ጠበበው
ገና ሲያጉረመርም የሚያንጠባጥበው?
አወይ አለማወቅ
የጎጆን አሰራር በቅጡ አለመማር
ቆርቆሮ ጣራውን
አጓጉል ቦታ ላይ
ሳይበሳው አይቀርም ሀሳብ አልባ ሚስማር!"
፣
ሕይወት ሁለት የተሰራበት ቁስ አካልና አዘጋጀጀቱ
ሀሳብ አልባ ሚስማር!
(በመጠን ይለያይ
ባለቆብ ተብሎ በክብር ይከፈል
በየተሰካበት
መቼም አንሶ አያውቅም
ጣራ ለመሸንቆር ሕይወት ለመፈልፈል!)
አለ አንዳንድ ሚስማር
ባለቆብ ተብሎ ቆቡን ያወለቀ
ና ድፈነን ሲሉት
ራሱ በበሳው ሾልኮ የወደቀ።
አለ አንዳንድ ሚስማር
በዛቻ በቁጭት
ገላምጠው የሚሉት
"ቀን የወጣልኝ ቀን እኔ እሱን እያርገኝ"
ቀጥ ባሉ መሃል
ቆንጅዬ ጣራ ላይ ተጣሞ የሚገኝ።
አለ አንዳንድ ሚስማር
የጨነቀው መሳይ መላ ቅጥ የሌለው
ጭንቅላቱ እና እግሩ
መሾል መዶልዶሙ የሚያመሳስለው።
፣
መንገድ ላይ የቀረ ምስኪንዬ ህጣን
ያዝማሪውን ግጥም
የልባችንን ጌጥ በመተርጎም ቀጣን።
"በየመንገዱ ላይ
ተረግጬ ምኖር
የሰው በረባሶ እኔ የሰው ጎማ
ሊያድሰኝ የመጣ
ኩርንችት ሲወጋኝ አሞኝ እንደዶማ
ከየሚስማሩ ጋር
አካሌና ነፍሴ ለክስ በወጣን
ሚስማር አድር ባዩ
አሳልፎ ሰጠን ለመዶሻ ሥልጣን።
፣
መዶሻ ቃል አባይ ባለሁለት ልሳን
"ሚስማር ላይ የተሾምኩ
እኔ ነኝ" እያለ መድረሻ እንዳልነሳን
ላይረገጥ ደፉ
ላንደርስ ደጃፉ
አሳልፎ ሰጠን ለባለመዳፉ።
፣
አንዱ አንዱን ሲሰይም
አንዱ ላንዱ ሲያዘም
ኃላፊነት ሽሽት እያጎበደደ
ኪሳራ እንዳጨቀው እድሜያችን ነጎደ።
አቤት ባይ ፍለጋ
ቢሰለች ቢመረን ነፍስ፣ እግር ማቅጠኑ
ኑሯችን ሌላ ነው
እንደሚስማሩ አይነት ልክ እንደመጠኑ።
ቀን እንጠብቃለን
ባለቆብ ነኝ ብሎ ቆቡን ያወለቀ
ራሱ በበሳው ሾልኮ በወደቀ!"
፣
ጠጪ ሦስት
"ተቀመጥ አዝማሪ
አታጎልድፍ ግጥም
በጨቀየ ሕይወት ባረጀ መሰንቆ
ሞትህ ሲሳብ እየው
በምትገርፈው ጭራ ሊሰቅልህ ነው አንቆ።
በሰቆቃ ግጥም
በደቃቃ ዜማ
አግዜሩን አትጨቅጭቅ ኑሮን አትነዝንዘው
ባይሆን ቁጭ በልና ሞትን ጠጅ ጋብዘው።"
፣
ሕይወት ሦስት የተሰራበት ቁስ አካል
ያረጀ መሰንቆ!
አዝማሪው ቁጭ አለ!
መሰንቆውን አየው።
ምስጥ የበላት እንጨት የዜማ መቃኛ
የታጠፈች ደጋን የዜማው መገኛ
በነዚህ መካከል
ተወጥሮ ያለ
የተበጣጠሰ የተንጨፈረረ ቀጭን የዜማ ክር
በሁለት ጽንፎች መሃል
(በኑሮና በሞት)
እንግልት ሲገርፈው
ተወጥሮ የሚያልቅ የሕይወት ምስክር።
አዝማሪው ቁጭ ብሎ
ወደ ሆነ ጥጋት መሰንቆውን ጥሎ
ግጥም ባቀበሉት
በሚንጫጩ መሃል እየፈነጠዘ
ከሞት ከኑሮ ጋር
ጠጅ ቺርስ እያለ መገባበዝ ያዘ።
፣
መንገድ ላይ የቀረ ምስኪንዬ ህጣን
ግጥም በመተርጎም ቆይቶ ሲቀጣን
ጠጪው መሃል ገብቶ
መሰንቆዋን ይዞ ወደ ውጭ ሲበር
ከዛ ሁሉ ሰው ውስጥ ያየውም አልነበር።
ህፃኑ እንዳነሳው
ልክ እንደመሰንቆው ደግሞም እንደጭራው
አንዱ በጣለው ነው ሌላው የሚሠራው።
@getem
@getem
@lula_al_greeko
(ያዴል ትዕዛዙ)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አሮጌ መሰንቆ
ሕይወት የገፋቸው ግጥም ሰጭ ጠጪዎች
ተቀምጠው ማያውቁ ቋሚ አዝማሪዎች
እና ደግሞ ተራ
የመንገድ ኩታራ...
እነኚህ ባሉበት
ግጥም ሰቆቃ ነው አሳር ሚበሉበት።
፣
ጠጪ አንድ
"ተቀበል አዝማሪ
መግፋት ቢከብደኝም
የእንጀራዬን ወፍጮ የሕይወቴን መጅ
እድሜ ለስካሬ
በተስፋ እኖራለሁ እየጠጣሁ ጠጅ።
እግዜር ይረሳኛል አይልም ድሀ አምልጦት
እምነቱን ይገምዳል ይፈትላል በእጦት።
ብቻ በቀደም ለት
እንዲህ እንደዛሬው መጠጫ አቶ ኪሴ
ቤት በጊዜ ገባሁ
ጨብጠው አገኘሁ
ሴት ልጄ ባሕር ዛፍ ሚስቴ ዳማ ከሴ።"
፣
ሕይወት አንድ የተሰራበት ቁስ አካል እና አዘገጃጀቱ
ነጭ ባሕር ዛፍ!
(ልክ እንደስሙና ልክ እንደታሪኩ
የባሕር ዛፍ ነገር ሁለት ነው መልኩ!)
ሳል ያሰቃየን ቀን
ይህን ነጭ ባህር ዛፍ መንደሬው ቀቅሎ
ፈውስ ነው ይለዋል
ሳምባህን አፍኖ "ጉነፋኑን ነቃቅሎ።"
ደግሞ እንደሰማነው
ባህር ዛፍ ተፈጥሮው ባህር ዛፍ አመሉ
የምድርን ሆድ መጦ
ለራሱ ሲፋፋ ሌላውን እፅዋት እድገት መከልከሉ።
፣
መንገድ ላይ የቀረ ምስኪንዬ ህጣን
መንገድ ዳር ተቀምጦ
ጠጅ ቤቱን እያየ
የግጥሙን አስኳል በመተርጎም ቀጣን።
"በየብርዱ ግንባር
ተሰጥቼ ምኖር
እኔ የዓለም ቅዳጅ የቀዬው እራፊ
ከቀን ጣቃ መሃል
ሳይመትሩ ቀደው
ቧጭሮኝ የምባክን የቀን ሽርፍራፊ
መኖርና ነፋስ
ነፍስያዬን ጨንቋት
ሳል እያጣደፈኝ ለጩኸት ባልበቃም
ፈውስ ነው አትበሉኝ
ስም በማቀያየር ሕይወት አይጠረቃም።
፣
እንደየባሕሩ እንደየዛፉ አቅም
ከደረቅ መሬት ላይ ፈውስ ስንለቅም
ሁለትዜ ሳትን
አንዴም ባሕር ዛፉን
ባሕር በሌለበት የብስ ላይ ስንተክለው
አንዴም ፈውስ ሽተን
ውኃችንን ግተን በ‘ሳት ስንቀቅለው።
እንዲህ ነው ልጅ መሆን እያደሩ ማነስ
ዳማ ከሴው ሲሻር
ባንዱ ነጩን ይዞ
በየተገኘው ላይ ጥውለጋን መነስነስ።
በየደረሱበት ኅልፈትን ማነፍነፍ
ስም እየቀየሩ ሁለቴ መሸነፍ።
እኔ ያለም ቅዳጅ
የቀዬው እራፊ
የዶፍ ብርዱ ወዳጅ
የሰው ትርፍራፊ
መጥቀሚያ መርፌና ክሬን አንጠልጥዬ
"እሰፋለሁ" ስል ነው የቀረሁ ተጥዬ።"
፣
ጠጪ ሁለት
"ተቀበል አዝማሪ
ምነው ይሄ ጎጆ
ምን ጠቢብ ቢያንፀው
ለመዳመን ሰፋ ማባራት ጠበበው
ገና ሲያጉረመርም የሚያንጠባጥበው?
አወይ አለማወቅ
የጎጆን አሰራር በቅጡ አለመማር
ቆርቆሮ ጣራውን
አጓጉል ቦታ ላይ
ሳይበሳው አይቀርም ሀሳብ አልባ ሚስማር!"
፣
ሕይወት ሁለት የተሰራበት ቁስ አካልና አዘጋጀጀቱ
ሀሳብ አልባ ሚስማር!
(በመጠን ይለያይ
ባለቆብ ተብሎ በክብር ይከፈል
በየተሰካበት
መቼም አንሶ አያውቅም
ጣራ ለመሸንቆር ሕይወት ለመፈልፈል!)
አለ አንዳንድ ሚስማር
ባለቆብ ተብሎ ቆቡን ያወለቀ
ና ድፈነን ሲሉት
ራሱ በበሳው ሾልኮ የወደቀ።
አለ አንዳንድ ሚስማር
በዛቻ በቁጭት
ገላምጠው የሚሉት
"ቀን የወጣልኝ ቀን እኔ እሱን እያርገኝ"
ቀጥ ባሉ መሃል
ቆንጅዬ ጣራ ላይ ተጣሞ የሚገኝ።
አለ አንዳንድ ሚስማር
የጨነቀው መሳይ መላ ቅጥ የሌለው
ጭንቅላቱ እና እግሩ
መሾል መዶልዶሙ የሚያመሳስለው።
፣
መንገድ ላይ የቀረ ምስኪንዬ ህጣን
ያዝማሪውን ግጥም
የልባችንን ጌጥ በመተርጎም ቀጣን።
"በየመንገዱ ላይ
ተረግጬ ምኖር
የሰው በረባሶ እኔ የሰው ጎማ
ሊያድሰኝ የመጣ
ኩርንችት ሲወጋኝ አሞኝ እንደዶማ
ከየሚስማሩ ጋር
አካሌና ነፍሴ ለክስ በወጣን
ሚስማር አድር ባዩ
አሳልፎ ሰጠን ለመዶሻ ሥልጣን።
፣
መዶሻ ቃል አባይ ባለሁለት ልሳን
"ሚስማር ላይ የተሾምኩ
እኔ ነኝ" እያለ መድረሻ እንዳልነሳን
ላይረገጥ ደፉ
ላንደርስ ደጃፉ
አሳልፎ ሰጠን ለባለመዳፉ።
፣
አንዱ አንዱን ሲሰይም
አንዱ ላንዱ ሲያዘም
ኃላፊነት ሽሽት እያጎበደደ
ኪሳራ እንዳጨቀው እድሜያችን ነጎደ።
አቤት ባይ ፍለጋ
ቢሰለች ቢመረን ነፍስ፣ እግር ማቅጠኑ
ኑሯችን ሌላ ነው
እንደሚስማሩ አይነት ልክ እንደመጠኑ።
ቀን እንጠብቃለን
ባለቆብ ነኝ ብሎ ቆቡን ያወለቀ
ራሱ በበሳው ሾልኮ በወደቀ!"
፣
ጠጪ ሦስት
"ተቀመጥ አዝማሪ
አታጎልድፍ ግጥም
በጨቀየ ሕይወት ባረጀ መሰንቆ
ሞትህ ሲሳብ እየው
በምትገርፈው ጭራ ሊሰቅልህ ነው አንቆ።
በሰቆቃ ግጥም
በደቃቃ ዜማ
አግዜሩን አትጨቅጭቅ ኑሮን አትነዝንዘው
ባይሆን ቁጭ በልና ሞትን ጠጅ ጋብዘው።"
፣
ሕይወት ሦስት የተሰራበት ቁስ አካል
ያረጀ መሰንቆ!
አዝማሪው ቁጭ አለ!
መሰንቆውን አየው።
ምስጥ የበላት እንጨት የዜማ መቃኛ
የታጠፈች ደጋን የዜማው መገኛ
በነዚህ መካከል
ተወጥሮ ያለ
የተበጣጠሰ የተንጨፈረረ ቀጭን የዜማ ክር
በሁለት ጽንፎች መሃል
(በኑሮና በሞት)
እንግልት ሲገርፈው
ተወጥሮ የሚያልቅ የሕይወት ምስክር።
አዝማሪው ቁጭ ብሎ
ወደ ሆነ ጥጋት መሰንቆውን ጥሎ
ግጥም ባቀበሉት
በሚንጫጩ መሃል እየፈነጠዘ
ከሞት ከኑሮ ጋር
ጠጅ ቺርስ እያለ መገባበዝ ያዘ።
፣
መንገድ ላይ የቀረ ምስኪንዬ ህጣን
ግጥም በመተርጎም ቆይቶ ሲቀጣን
ጠጪው መሃል ገብቶ
መሰንቆዋን ይዞ ወደ ውጭ ሲበር
ከዛ ሁሉ ሰው ውስጥ ያየውም አልነበር።
ህፃኑ እንዳነሳው
ልክ እንደመሰንቆው ደግሞም እንደጭራው
አንዱ በጣለው ነው ሌላው የሚሠራው።
@getem
@getem
@lula_al_greeko
👍2
እንዲህ ነኝ!(ልዑል ሀይሌ)
“እንዴት ነህ?” ከምትሉ
እስቲ እንደዚህ ሁኑ!
.
የቁስሌን መጠን ቁሰሉና ለኩ ፤
የሚያሳክከኝን ውሰዱና እከኩ፤
የሚያመኝን ሕመም ታመሙና ኑሩት፤
የልቤን ፍላሎት
አይገልፀውምና እንዲሁ ሲናገሩት።
.
“እንዴት ነህ?” ከምትሉ
እስቲ እንደዚህ ሁኑ!
.
’ሚነፍሰውን ንፋስ
በጎኔ ሚዘልቀው በጎናችሁ አዝልቁት፤
’ሚዘንበውን ዝናብ
’ሚያበሰብሰኝን በጉንጫችሁ አውርዱት፤
.
የሚያንገበግበኝ
የወዳጄን ክህደት በወዳጅ ተካዱ፤
እሾህ ላይ ስራመድ በእሾህ ላይ ሂዱ።
.
ያኔ ነው ምታውቁት
የኔን የሕይወት ፈር፤
“ደህና ነው” በሚል ቃል ይህ ሁሉ ሲሰፈር።
፲፪.፩.፲፩ ዓ.ም.
@getem
@getem
@gebriel_19
“እንዴት ነህ?” ከምትሉ
እስቲ እንደዚህ ሁኑ!
.
የቁስሌን መጠን ቁሰሉና ለኩ ፤
የሚያሳክከኝን ውሰዱና እከኩ፤
የሚያመኝን ሕመም ታመሙና ኑሩት፤
የልቤን ፍላሎት
አይገልፀውምና እንዲሁ ሲናገሩት።
.
“እንዴት ነህ?” ከምትሉ
እስቲ እንደዚህ ሁኑ!
.
’ሚነፍሰውን ንፋስ
በጎኔ ሚዘልቀው በጎናችሁ አዝልቁት፤
’ሚዘንበውን ዝናብ
’ሚያበሰብሰኝን በጉንጫችሁ አውርዱት፤
.
የሚያንገበግበኝ
የወዳጄን ክህደት በወዳጅ ተካዱ፤
እሾህ ላይ ስራመድ በእሾህ ላይ ሂዱ።
.
ያኔ ነው ምታውቁት
የኔን የሕይወት ፈር፤
“ደህና ነው” በሚል ቃል ይህ ሁሉ ሲሰፈር።
፲፪.፩.፲፩ ዓ.ም.
@getem
@getem
@gebriel_19
''እንፋሎት''
---------
በፀሐይ ወበቅ ተለብልቦ
በስሜት እሳት ተከቦ
እንደሚጎፈላ በ'ሳት ግመት
እንደፈላ ትኩስ ወተት
አለ ለካ..የወዳጅም ተን እንፋሎት
ክዳን ሲገፋ እንጂ፣ሲርቅ የማያዩት
.
«ሚኪ እንዳለ»
@getem
@getem
@gebriel_19
---------
በፀሐይ ወበቅ ተለብልቦ
በስሜት እሳት ተከቦ
እንደሚጎፈላ በ'ሳት ግመት
እንደፈላ ትኩስ ወተት
አለ ለካ..የወዳጅም ተን እንፋሎት
ክዳን ሲገፋ እንጂ፣ሲርቅ የማያዩት
.
«ሚኪ እንዳለ»
@getem
@getem
@gebriel_19
ልመና
መቅደሱ ስር ሆኜ እንባዬን ሳነባ
መፈጠሬን ስረግም ሆዴንም ሳባባ
አንዱ ጠጋ አለ ከልቡ ሊያወራኝ
ላስቸግርህ! አለ ፈቃዴን ጠየቀኝ
እሺ! አልኩ ከልቤ
ችግሬንም ስማኝ
እራትም አልበላዉ ለዛሬም የለኝ
ካለህ ላይ ቆንጥረህ
እባክህ አካፍለኝ?
ድንጋጤ ሞላኝ ልቤም ተሸበረ
ላይበቃው በመስጠቴ
ውስጤ እያፈረ
...ይበቃል አለ ውስጡ እየፈነደቀ
የሱን ደስታ አይቼ ምኔ ተደነቀ
ችግር ላይ መሆኔን
ልቤም እያወቀ
እግዜር ይስጥህ! በወጣው ይተካ!
መረቀኝ ከልቡ በጌታው ተመካ!
ይስጠኝ መና እሱ
ሳይወስድ መልሶ
ይምራኝ በመንገዱ
ይውሰደኝ ቀልሶ
ይህን እያሰብኩኝ!
ጭንቀቴን ረሳውኝ!
ማማረሬን ተውኩኝ!
አዲስ ቀን ጀመርኩኝ!
ገጣሚ ዳዊት አለሙ/dave ak
@getem
@getem
@gebriel_19
መቅደሱ ስር ሆኜ እንባዬን ሳነባ
መፈጠሬን ስረግም ሆዴንም ሳባባ
አንዱ ጠጋ አለ ከልቡ ሊያወራኝ
ላስቸግርህ! አለ ፈቃዴን ጠየቀኝ
እሺ! አልኩ ከልቤ
ችግሬንም ስማኝ
እራትም አልበላዉ ለዛሬም የለኝ
ካለህ ላይ ቆንጥረህ
እባክህ አካፍለኝ?
ድንጋጤ ሞላኝ ልቤም ተሸበረ
ላይበቃው በመስጠቴ
ውስጤ እያፈረ
...ይበቃል አለ ውስጡ እየፈነደቀ
የሱን ደስታ አይቼ ምኔ ተደነቀ
ችግር ላይ መሆኔን
ልቤም እያወቀ
እግዜር ይስጥህ! በወጣው ይተካ!
መረቀኝ ከልቡ በጌታው ተመካ!
ይስጠኝ መና እሱ
ሳይወስድ መልሶ
ይምራኝ በመንገዱ
ይውሰደኝ ቀልሶ
ይህን እያሰብኩኝ!
ጭንቀቴን ረሳውኝ!
ማማረሬን ተውኩኝ!
አዲስ ቀን ጀመርኩኝ!
ገጣሚ ዳዊት አለሙ/dave ak
@getem
@getem
@gebriel_19
ጠብቆ ሚበላ
——————
እረኛውን አምኖ፣ተኩላን መስጋቱ
ያደርገዋል የዋህ፣በግን በሕይወቱ
የዋህነት አድጎ፣ካለፈ ከደርዙ
ጅልነት ይሆናል፣መዳረሻ ጠርዙ
ማ'እንዳለ ከጎኑ፣በጉ መቼ ያውቃል
ከበዪ ለመዳን፣በ'በይ ይጠበቃል
ጠላትን ፍራቻ፣ከጠላት ይውላል
ግና ምን ያደርጋል !!!
የኋላ ኋላውን፣ሰውነቱ ያድጋል
በተኩላው ሳይሆን...
ዘላልም ባመነው፣በረኛው ይበላል
ቆመው ከጎናችን.…
እንቅልፍን ሳይተኙ ፣ ተግተው ሚጠብቁን
ለካስ አስበው ነው .…
ከሌሎች አድነው፣እነሱው ሊበሉን
እሩቅ የምናየው፣በቅርቡ ሲተካ
መውደድ ለራስ ጥቅም፣ በሚለው ሲለካ
የኔ በግ እያለ..…
ከጠላት ሚጠብቅ፣ጠላት አለ ለካ !!!
.
( ሚኪ እንዳለ )
@getem
@getem
——————
እረኛውን አምኖ፣ተኩላን መስጋቱ
ያደርገዋል የዋህ፣በግን በሕይወቱ
የዋህነት አድጎ፣ካለፈ ከደርዙ
ጅልነት ይሆናል፣መዳረሻ ጠርዙ
ማ'እንዳለ ከጎኑ፣በጉ መቼ ያውቃል
ከበዪ ለመዳን፣በ'በይ ይጠበቃል
ጠላትን ፍራቻ፣ከጠላት ይውላል
ግና ምን ያደርጋል !!!
የኋላ ኋላውን፣ሰውነቱ ያድጋል
በተኩላው ሳይሆን...
ዘላልም ባመነው፣በረኛው ይበላል
ቆመው ከጎናችን.…
እንቅልፍን ሳይተኙ ፣ ተግተው ሚጠብቁን
ለካስ አስበው ነው .…
ከሌሎች አድነው፣እነሱው ሊበሉን
እሩቅ የምናየው፣በቅርቡ ሲተካ
መውደድ ለራስ ጥቅም፣ በሚለው ሲለካ
የኔ በግ እያለ..…
ከጠላት ሚጠብቅ፣ጠላት አለ ለካ !!!
.
( ሚኪ እንዳለ )
@getem
@getem
የልቤ ትርታ
እኔ ካንች ስርቅ ይሰማሻል ደስታ
ኣይኔን ካላየሽው ይጠፋል ትውስታ?
ከኔ ጋር የሆነው ይቀበራል ላፍታ
አይመስለኝም ነበር የልቤ ትርታ
እኔማ በኔ ቤት
ሃሳብ ኣስሬበት
ምኞት እንደስጋ በውኔ እያየሁት
ላገኝሽ ነው ብየ ጥዋት ካነጋሁት
ሲመሽ ገና ገባኝ ጨረቃን እንዳየሁት
ተፃፈ በከድር
የካቲት 2011
@getem
@getem
@gebriel_19
እኔ ካንች ስርቅ ይሰማሻል ደስታ
ኣይኔን ካላየሽው ይጠፋል ትውስታ?
ከኔ ጋር የሆነው ይቀበራል ላፍታ
አይመስለኝም ነበር የልቤ ትርታ
እኔማ በኔ ቤት
ሃሳብ ኣስሬበት
ምኞት እንደስጋ በውኔ እያየሁት
ላገኝሽ ነው ብየ ጥዋት ካነጋሁት
ሲመሽ ገና ገባኝ ጨረቃን እንዳየሁት
ተፃፈ በከድር
የካቲት 2011
@getem
@getem
@gebriel_19
ልብኛ ጉዞ(ልዑል ሀይሌ)
ምስል:-ከ Zuki Shewa ግድግዳ የተዘረፈ
በጉዞዬ መሐል
ምስልሽ እየታየኝ ፅልመት ማይጋርደው፤
መች ይታወቀኛል
የመንገዱ ርዝመት እልፍ ምራመደው፤
.
እኔ መንገደኛው
እሾኅ እየወጋኝ በጨለማው መንገድ፤
አንቺን እያሰብኩኝ
ሰርክ እማፀናለሁ ህመሜን ለመልመድ፤
.
ይህ ልቤ
ካሰበበት ሊደርስ
ለሚሄደው እርምጃ ለሚሄደው ጉዞ፤
መታመም ባይቀርም
ስቃይ ይሻገራል ሚወደውን ይዞ፤
.
(ይለኛል ይህ ልቤ...)
ተነስ አንተ አካሌ
ይልቅ ተነስልኝ
መጓዝ ላይቀርልህ
እሾኅ ላይቀርልህ ህመም ልመድልኝ፤
.
ተላመድ ከስቃይ
ተላመድ ከቁስል፤
በቆሰለው እግርህ
ሳለው ያንተን ምስል፤
.
ሳለው በጨለማ
ሳለው በመንገዱ፤
ንጋት ይገልጠዋል
የሚወዱትን ሰው
ብለው ሲራመዱ፤
(ይለኛል ይህ ልቤ...)
.
ተራመድ!
ወደፊት
ተወው ያን እንቅፋት፤
ናፍቆት ትዝታህን
አሸንፈህ አልፈህ
ፍቅርህን እቀፋት፤
.
ይለኛል
ይህ ልቤ ከእግር የተጣላ፤
አካሌን ሊያስከዳኝ ሊያላምደኝ ሌላ፤
.
ይህ ልቤ ብርቱ ነው
አለት ነው ያነፅኩት፤
ግን እንዴት ልመነው
ስንቴ ከሳት ጥዶኝ እየተማፀንኩት
፲፬-፰-፳፻፲፩ ዓ.ም.
@getem
@getem
@Lula_al_greeko
ምስል:-ከ Zuki Shewa ግድግዳ የተዘረፈ
በጉዞዬ መሐል
ምስልሽ እየታየኝ ፅልመት ማይጋርደው፤
መች ይታወቀኛል
የመንገዱ ርዝመት እልፍ ምራመደው፤
.
እኔ መንገደኛው
እሾኅ እየወጋኝ በጨለማው መንገድ፤
አንቺን እያሰብኩኝ
ሰርክ እማፀናለሁ ህመሜን ለመልመድ፤
.
ይህ ልቤ
ካሰበበት ሊደርስ
ለሚሄደው እርምጃ ለሚሄደው ጉዞ፤
መታመም ባይቀርም
ስቃይ ይሻገራል ሚወደውን ይዞ፤
.
(ይለኛል ይህ ልቤ...)
ተነስ አንተ አካሌ
ይልቅ ተነስልኝ
መጓዝ ላይቀርልህ
እሾኅ ላይቀርልህ ህመም ልመድልኝ፤
.
ተላመድ ከስቃይ
ተላመድ ከቁስል፤
በቆሰለው እግርህ
ሳለው ያንተን ምስል፤
.
ሳለው በጨለማ
ሳለው በመንገዱ፤
ንጋት ይገልጠዋል
የሚወዱትን ሰው
ብለው ሲራመዱ፤
(ይለኛል ይህ ልቤ...)
.
ተራመድ!
ወደፊት
ተወው ያን እንቅፋት፤
ናፍቆት ትዝታህን
አሸንፈህ አልፈህ
ፍቅርህን እቀፋት፤
.
ይለኛል
ይህ ልቤ ከእግር የተጣላ፤
አካሌን ሊያስከዳኝ ሊያላምደኝ ሌላ፤
.
ይህ ልቤ ብርቱ ነው
አለት ነው ያነፅኩት፤
ግን እንዴት ልመነው
ስንቴ ከሳት ጥዶኝ እየተማፀንኩት
፲፬-፰-፳፻፲፩ ዓ.ም.
@getem
@getem
@Lula_al_greeko
Forwarded from ቅንድል ኢትዮጵያ (Ermiyas Dejene)
ቀንዲል ዲጂታል መፅሔት.pdf
6 MB