ላንቺ ብፅፍ ግጥም
ቆረጥኩኝ የሴት ጥም
እንደው ባየሺልኝ
1 አንቺ ስትሄጂ ናፍቀሺኛል ብልሽ
በስንኜ በኩል
የእንስት ጋጋታ ህይወቴን ሞላልሽ
የምን በትዝታ ሰክሮ መንገዳገድ
ሀሳብ ውሎ ይግባ በብዕሬ መንገድ
(ይህንን አትርሺ)
ሰው በቃል ይረሳል
ሰው በቃል ይፈርሳል ሰው በቃል ይሰራል
ባለቀሰበትም ድንኳን ይሞሸራል
By @Absari_seven
@getem
@getem
ቆረጥኩኝ የሴት ጥም
እንደው ባየሺልኝ
1 አንቺ ስትሄጂ ናፍቀሺኛል ብልሽ
በስንኜ በኩል
የእንስት ጋጋታ ህይወቴን ሞላልሽ
የምን በትዝታ ሰክሮ መንገዳገድ
ሀሳብ ውሎ ይግባ በብዕሬ መንገድ
(ይህንን አትርሺ)
ሰው በቃል ይረሳል
ሰው በቃል ይፈርሳል ሰው በቃል ይሰራል
ባለቀሰበትም ድንኳን ይሞሸራል
By @Absari_seven
@getem
@getem
❤61🔥12👍5😱2
ወደግራ ወድቆ
ፍቅራችን ዳመራው
የትዝታሽ ጭሱን ናፍቆት ሰማይ ጠራው
እሄዳለሁ ብዬ ሶዶ ወይ ጉራጌ
አንቺ የሌለሽበት
መስቀል እንዴት ላክብር እንደምን አድርጌ
By @Absari_seven
@getem
@getem
ፍቅራችን ዳመራው
የትዝታሽ ጭሱን ናፍቆት ሰማይ ጠራው
እሄዳለሁ ብዬ ሶዶ ወይ ጉራጌ
አንቺ የሌለሽበት
መስቀል እንዴት ላክብር እንደምን አድርጌ
By @Absari_seven
@getem
@getem
❤47😁14👎2
ቢታነፅ ቢወቀር!
(በእውቀቱ ስዩም)
እኔም አንድ ሰሞን
ልክ እንደ ሰለሞን
"ሁሉም ከንቱ ከንቱ ንፋስን መከተል
ላይጥሉ መታገል: ላይከብሩ መባተል"
እያልሁ አጨልሜ
በራሴ ለግሜ: እፈላሰፍ ነበር!
ከዚያ አንቺን አገኘሁ
በጓሮ በር በኩል: ሰለሞኔን ሸኘሁ
መፈጠሬን ወደድሁ
ንፋስ አሳድጄ እንደ ቆቅ አጠመድሁ
ከፀሀይዋ በታች: ግልገል ፀሀይ ፈጠርሁ
ለኦናው አምፖሌ: ብርሀን አበደርሁ
ማቅ የነበረው ጨርቅ: ሸማ ሆኖ ቆየኝ
"ከንቱ የነበረው: "አንቱ" ሆኖ ታየኝ!
ለካስ...
ጠቢብ ቢያስተምረው
መከራ ቢመክረው
አካሉና ልቡ: ቢታነፅ ቢወቀር
ሰው አቅሙን አያውቅም: ካልወደደ በቀር!
@getem
@getem
@paappii
(በእውቀቱ ስዩም)
እኔም አንድ ሰሞን
ልክ እንደ ሰለሞን
"ሁሉም ከንቱ ከንቱ ንፋስን መከተል
ላይጥሉ መታገል: ላይከብሩ መባተል"
እያልሁ አጨልሜ
በራሴ ለግሜ: እፈላሰፍ ነበር!
ከዚያ አንቺን አገኘሁ
በጓሮ በር በኩል: ሰለሞኔን ሸኘሁ
መፈጠሬን ወደድሁ
ንፋስ አሳድጄ እንደ ቆቅ አጠመድሁ
ከፀሀይዋ በታች: ግልገል ፀሀይ ፈጠርሁ
ለኦናው አምፖሌ: ብርሀን አበደርሁ
ማቅ የነበረው ጨርቅ: ሸማ ሆኖ ቆየኝ
"ከንቱ የነበረው: "አንቱ" ሆኖ ታየኝ!
ለካስ...
ጠቢብ ቢያስተምረው
መከራ ቢመክረው
አካሉና ልቡ: ቢታነፅ ቢወቀር
ሰው አቅሙን አያውቅም: ካልወደደ በቀር!
@getem
@getem
@paappii
❤63🔥20👍6🎉1
ቃል ከአፋቸው ሳይወጣ
ፍቅር ተሰናብቶ መለያየት መጣ
ቻው እንኳን ሳይሉኝ
ሁሉም አገለሉኝ
እኔ ብቻ ሆነ እኔን የወደደው
እሱስ ተራው ደርሶ መች ይሆን ሚሄደው
By @Absari_seven
@getem
@getem
ፍቅር ተሰናብቶ መለያየት መጣ
ቻው እንኳን ሳይሉኝ
ሁሉም አገለሉኝ
እኔ ብቻ ሆነ እኔን የወደደው
እሱስ ተራው ደርሶ መች ይሆን ሚሄደው
By @Absari_seven
@getem
@getem
❤37🤩9🔥5
ራሱ’ንደማይጠጣ - የውሃ ማሰሮ፣
መሆን ላልተቻለው - ክው ያለ ጉሮሮ፤
አስመሳይ ደጋጎች - ውሃ ሰጡት’ና፣
የሞት ሞቱን ሲኖር - ችግሩ እንደጠና፤
ጉሮሮ ማሰሮ - ተመሳስሎባቸው፣
ያጠጡትን ቀድተው - መውሰድ ላቃታቸው፤
ረሃብ አንጎራጉሮ - ለለመደው ውሃ፣
ሰጥቶ ተቀባዮች አስቀየመልሃ!
(የሞገሴ ልጅ)
@eyadermoges
@getem
@getem
@getem
መሆን ላልተቻለው - ክው ያለ ጉሮሮ፤
አስመሳይ ደጋጎች - ውሃ ሰጡት’ና፣
የሞት ሞቱን ሲኖር - ችግሩ እንደጠና፤
ጉሮሮ ማሰሮ - ተመሳስሎባቸው፣
ያጠጡትን ቀድተው - መውሰድ ላቃታቸው፤
ረሃብ አንጎራጉሮ - ለለመደው ውሃ፣
ሰጥቶ ተቀባዮች አስቀየመልሃ!
(የሞገሴ ልጅ)
@eyadermoges
@getem
@getem
@getem
❤19👍14🔥1
ዛሬ ሌላ ሰው ነኝ።
ያኔ ትንሽ ሆኜ-
በእድሜዬ ለጋ - በበሓሪ ችኩል፣
አፍንጫ አሽትቻለሁ፣
ቀድሞኝ ከበሰለው - ለመታየት እኩል።
ልጅነትን ሳልፈው-
ሌላን ማየት ትቼ - ራሴን ዐየሁ እና፣
ገደብ ሰራሁለት፣
ጉጉቴ ልክ አልፎ -ስጎድል እንዳይቀና።
ልልሽ የፈለግሁት-
አንቺ ላታስቢኝ አትበይ “ረስተኸኛል”፣
የሰርግሽን ፎቶ-
ከልቤ ሳደንቀው እራሴም ገርሞኛል።
ምክንያት፣...
ያኔ ወጣትነት - ኩራት የኮፈሰኝ፣
ትእቢት ላንዳፍታ - ወስዶ የመለሰኝ፤
እልህ እየጋተ - ምላጭ የሚያስውጠኝ፣
“ዛሬ ብቻ” ባይ ኅዝብ - አስሶ እሚመርጠኝ፤
ዛሬ...
አንቺ የኖርሽውን - ዘመን የኖርኩ እኔ፣
እራሴን ያስተማርኩ - በሕይወት ጠመኔ፤
አንቺ “ፈልጉኝ” ባይ - እኔ ራሴን መሪ፣
አንቺ ላይሽ ፋኖስ - እኔ ውስጤ በሪ፤
ከመንገድሽ እሩቅ - መንገዴ ወስዶኛል፣
ሺህ ግዜ አግብተሽ - ሺህ ግዜ ብትፈቺ ምን ያናድደኛል?
በርቺ 😐
@eyadermoges
@getem
@getem
@getem
ያኔ ትንሽ ሆኜ-
በእድሜዬ ለጋ - በበሓሪ ችኩል፣
አፍንጫ አሽትቻለሁ፣
ቀድሞኝ ከበሰለው - ለመታየት እኩል።
ልጅነትን ሳልፈው-
ሌላን ማየት ትቼ - ራሴን ዐየሁ እና፣
ገደብ ሰራሁለት፣
ጉጉቴ ልክ አልፎ -ስጎድል እንዳይቀና።
ልልሽ የፈለግሁት-
አንቺ ላታስቢኝ አትበይ “ረስተኸኛል”፣
የሰርግሽን ፎቶ-
ከልቤ ሳደንቀው እራሴም ገርሞኛል።
ምክንያት፣...
ያኔ ወጣትነት - ኩራት የኮፈሰኝ፣
ትእቢት ላንዳፍታ - ወስዶ የመለሰኝ፤
እልህ እየጋተ - ምላጭ የሚያስውጠኝ፣
“ዛሬ ብቻ” ባይ ኅዝብ - አስሶ እሚመርጠኝ፤
ዛሬ...
አንቺ የኖርሽውን - ዘመን የኖርኩ እኔ፣
እራሴን ያስተማርኩ - በሕይወት ጠመኔ፤
አንቺ “ፈልጉኝ” ባይ - እኔ ራሴን መሪ፣
አንቺ ላይሽ ፋኖስ - እኔ ውስጤ በሪ፤
ከመንገድሽ እሩቅ - መንገዴ ወስዶኛል፣
ሺህ ግዜ አግብተሽ - ሺህ ግዜ ብትፈቺ ምን ያናድደኛል?
በርቺ 😐
@eyadermoges
@getem
@getem
@getem
❤26👍20🔥1😁1
የማመንታት ፍቅር
ልሂድ ወይስ ልቅር
(ያለበት)
ጓዝሽን ጠቅልለሽ በስንብትሽ እለት
ደግሞ ተመልሶ
ከበቃኸኝ በኃላ ካልበላሁ ማለት
(ምን ይሉታል አሁን)
ተፍተሺኝ አንቅረሽ
ጥላቻን አፍቅረሽ
ባፍንጫሽ ወጥቼ
ለፍቺያችን ድግስ የወይን ጠጅ ጠጥቼ
(ችርስ ተባብለን)
ወይ መተሽ አትመጪ ወይ ቀርተሽ አትቀሪ
ድንገት ትገኛለሽ ለፍቅር ከፊቴ ስትደነቀሪ
By @Absari_seven
@getem
@getem
ልሂድ ወይስ ልቅር
(ያለበት)
ጓዝሽን ጠቅልለሽ በስንብትሽ እለት
ደግሞ ተመልሶ
ከበቃኸኝ በኃላ ካልበላሁ ማለት
(ምን ይሉታል አሁን)
ተፍተሺኝ አንቅረሽ
ጥላቻን አፍቅረሽ
ባፍንጫሽ ወጥቼ
ለፍቺያችን ድግስ የወይን ጠጅ ጠጥቼ
(ችርስ ተባብለን)
ወይ መተሽ አትመጪ ወይ ቀርተሽ አትቀሪ
ድንገት ትገኛለሽ ለፍቅር ከፊቴ ስትደነቀሪ
By @Absari_seven
@getem
@getem
❤32👍11🔥4
ቆርጦልኝ ነበረ ነግሬሽ የልቤን ወድሻለሁ ብዬ
የምትወጂኝ መስሎኝ ስጠብቅሽ ቀረሁ ካደርኩበት ውዬ
ነካክተሽ ነካክሽ ልቤን አደረግሽው የፍቅርሽ ምርኮኛ
የማትወጂኝ ከሆን ለምን ቀሰቀስሽው ይቅር እንደተኛ
አይቀርም አንድ ቀን ያፈቀረሽ ልቤ የጎኑን ማግኘቱ
ህይወት ይቀጥላል ምን ልቤ ቢደክም አንቺን በማጣቱ
አገኘሽኝ እንጂ ሆኜ ያንቺ ወዳጅ
ከፍቅርሽ አለም ውስጥ
ሳላውቀው ገብቼ እንደ ባህር ሰርጓጅ
ግን ...
ያሳሰበኝ ፍቅር
ካንቺ ስር ያዋለኝ እንዲህ እንደከረረ
ሌላ ሲያይሽ ጊዜ ቀንቼ ነበረ
አፈቀርኩሽ ያልኩት
የኔ ያልኩትን ሰው በሌላ ሲታቀፍ
እንዴት ብዬ ልለፍ
የመነጠቅ መንፈስ
ውስጤን እንገብግቦት አላመጣሁሽም
እውነቱን ስነግርሽ
ቀንቼ ነው እንጂ አላፈቀርኩሽም
አልልሽም ይህን ቃሌን ድፍረት የለኝ የምልበት
ያጠፋዋልና የወንድነት ልኩን ይህን ያልኩሽ እለት
እንደገባኝ ቢሆን ከዚህ ሁሉ ነገር
ቅናት መንፈስ እንጂ አልነበረም ማፍቀር
ዮርዳኖስ @JorDanos7
@getem
@getem
@getem
የምትወጂኝ መስሎኝ ስጠብቅሽ ቀረሁ ካደርኩበት ውዬ
ነካክተሽ ነካክሽ ልቤን አደረግሽው የፍቅርሽ ምርኮኛ
የማትወጂኝ ከሆን ለምን ቀሰቀስሽው ይቅር እንደተኛ
አይቀርም አንድ ቀን ያፈቀረሽ ልቤ የጎኑን ማግኘቱ
ህይወት ይቀጥላል ምን ልቤ ቢደክም አንቺን በማጣቱ
አገኘሽኝ እንጂ ሆኜ ያንቺ ወዳጅ
ከፍቅርሽ አለም ውስጥ
ሳላውቀው ገብቼ እንደ ባህር ሰርጓጅ
ግን ...
ያሳሰበኝ ፍቅር
ካንቺ ስር ያዋለኝ እንዲህ እንደከረረ
ሌላ ሲያይሽ ጊዜ ቀንቼ ነበረ
አፈቀርኩሽ ያልኩት
የኔ ያልኩትን ሰው በሌላ ሲታቀፍ
እንዴት ብዬ ልለፍ
የመነጠቅ መንፈስ
ውስጤን እንገብግቦት አላመጣሁሽም
እውነቱን ስነግርሽ
ቀንቼ ነው እንጂ አላፈቀርኩሽም
አልልሽም ይህን ቃሌን ድፍረት የለኝ የምልበት
ያጠፋዋልና የወንድነት ልኩን ይህን ያልኩሽ እለት
እንደገባኝ ቢሆን ከዚህ ሁሉ ነገር
ቅናት መንፈስ እንጂ አልነበረም ማፍቀር
ዮርዳኖስ @JorDanos7
@getem
@getem
@getem
👍35❤25🤩6🔥3
ግጥም ነው ምትመስዪው!
---------------------------------------
ከፊደል ማሳ ላይ ቃላት ለሚቃርም
ካገኘም ከትቦ እያደር ሚያርም÷
በአርኬው መባቻ በመድፋት አባዜ
ከሃሳብ ባህር ላይ ሰጥሞ በትካዜ÷
በብዕሩ እንባ ስንኞች ሲቋጥር
ቤቱን በመዘንጋት ቤት ለመምታት ሚጥር÷
እቴ አትሞኚ ከቁብ ለማይቆጥርሽ
በፍቅር አጊጠሽ አምሮብሽ ቢያይሽ÷
በቃላት ስደራ የተሽቀረቀረ
በታሪክ ፍሰቱ ጎልቶ የዳበረ÷
ግጥም ነው ምትመስዪው
መምቻና መድፊያው ፍፃሜው ያማረ::
By @Abuugida
@getem
@getem
@getem
---------------------------------------
ከፊደል ማሳ ላይ ቃላት ለሚቃርም
ካገኘም ከትቦ እያደር ሚያርም÷
በአርኬው መባቻ በመድፋት አባዜ
ከሃሳብ ባህር ላይ ሰጥሞ በትካዜ÷
በብዕሩ እንባ ስንኞች ሲቋጥር
ቤቱን በመዘንጋት ቤት ለመምታት ሚጥር÷
እቴ አትሞኚ ከቁብ ለማይቆጥርሽ
በፍቅር አጊጠሽ አምሮብሽ ቢያይሽ÷
በቃላት ስደራ የተሽቀረቀረ
በታሪክ ፍሰቱ ጎልቶ የዳበረ÷
ግጥም ነው ምትመስዪው
መምቻና መድፊያው ፍፃሜው ያማረ::
By @Abuugida
@getem
@getem
@getem
❤29👍4😁1
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
--------------------------
አንቺ ስትስቂ
ከሰማይ ላይ ወፎች፣
እስከ ምድር ሰዎች፣
የገነት በር ደጆች፣
የቅዱሳን ፊቶች፣
አምረው ያበራሉ፤
ደስታን ያገኛሉ።
ትልቁ ጎልያድ
በሳቅሽ ተማሎ፣
ብላቴነው ዳዊት
ጠጠሮቹን ጥሎ፣
ያንቺን ሳቅ ነበረ
ተቃቅፈው ሚሰሙት፣
ፈገግታሽን ነበር
ሚያስቡት ሚያልሙት።
አንቺ ስትስቂ
ፀሃይ ከጨርቃ፣
ብርሃን ከጨለማ፣
ሰማይ ከምድር ጋ፣
ወፎች ከአረዊቶች፣
ክረምት ሳይቀር በጋ፣
አንድ አምሳል ነበሩ፣
በሳቅሽ ግዞት ውስጥ
አንድ ላይ ሚኖሩ።
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ጎልያድ አቅራራ
ዳዊት ላይ ደነፋ፣
አባቶች ተከፍተው
መቋሚያ አነሱ፣
እንድትስቂላቸዉ
ፆም ፀሎት ሊያደርሱ።
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ሰማይ አለቀሰ፣
ፀሃይ ተናደደች፣
ነፍሳትን አቃጥላ
ጨለማን ሰደደች።
እኔም ስጠባበቅ
በምኞት በተስፋ፣
ሳቅሽን ናፍቄ
ሳቅሽን ተርቤ
ግዜ ይዞኝ ጠፋ
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
@getem
@getem
@paappii
--------------------------
አንቺ ስትስቂ
ከሰማይ ላይ ወፎች፣
እስከ ምድር ሰዎች፣
የገነት በር ደጆች፣
የቅዱሳን ፊቶች፣
አምረው ያበራሉ፤
ደስታን ያገኛሉ።
ትልቁ ጎልያድ
በሳቅሽ ተማሎ፣
ብላቴነው ዳዊት
ጠጠሮቹን ጥሎ፣
ያንቺን ሳቅ ነበረ
ተቃቅፈው ሚሰሙት፣
ፈገግታሽን ነበር
ሚያስቡት ሚያልሙት።
አንቺ ስትስቂ
ፀሃይ ከጨርቃ፣
ብርሃን ከጨለማ፣
ሰማይ ከምድር ጋ፣
ወፎች ከአረዊቶች፣
ክረምት ሳይቀር በጋ፣
አንድ አምሳል ነበሩ፣
በሳቅሽ ግዞት ውስጥ
አንድ ላይ ሚኖሩ።
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ጎልያድ አቅራራ
ዳዊት ላይ ደነፋ፣
አባቶች ተከፍተው
መቋሚያ አነሱ፣
እንድትስቂላቸዉ
ፆም ፀሎት ሊያደርሱ።
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ሰማይ አለቀሰ፣
ፀሃይ ተናደደች፣
ነፍሳትን አቃጥላ
ጨለማን ሰደደች።
እኔም ስጠባበቅ
በምኞት በተስፋ፣
ሳቅሽን ናፍቄ
ሳቅሽን ተርቤ
ግዜ ይዞኝ ጠፋ
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
ያ ሳቅሽ ሲጠፋ
@getem
@getem
@paappii
❤84😁5🔥4👎1
ፍቅር አለኝ ለአንተ!
-----------------------------
አደመጥሁኝ ቅኔ መልሴ መልሼ፣
ሙዚቃውን ሰማሁ ዓለሙን አስሼ።
ዜማ ሰለለብኝ ሥዕል ደበዘዘ ግጥም አነከሰ፤
ባሳይህ... ብኖረው... የልቤ አልደረሰ።
(አንደ ምን ልግለጸው?)
ጥበብ ያሳነሰው .
ቋንቋ ያኮሰሰው .
ፍቅር አለኝ ለአንተ፣
በፍጥረት ዘመን ልክ እየተጎተተ
አስከ ዓለም ፍጻሜ ደግሞ 'ሚዘረጋ፣
ብኖርም ባንኖርም
ምጽአት የሚጠብቅ በነፍስም በሥጋ።
ፍቅር አለኝ ላንተ
ምድር የሚሞላ፣
ከእግዜር የሚያስታርቅ ከእግዜር የሚያጣላ።
By Meron Ghetnet
@getem
@getem
@getem
-----------------------------
አደመጥሁኝ ቅኔ መልሴ መልሼ፣
ሙዚቃውን ሰማሁ ዓለሙን አስሼ።
ዜማ ሰለለብኝ ሥዕል ደበዘዘ ግጥም አነከሰ፤
ባሳይህ... ብኖረው... የልቤ አልደረሰ።
(አንደ ምን ልግለጸው?)
ጥበብ ያሳነሰው .
ቋንቋ ያኮሰሰው .
ፍቅር አለኝ ለአንተ፣
በፍጥረት ዘመን ልክ እየተጎተተ
አስከ ዓለም ፍጻሜ ደግሞ 'ሚዘረጋ፣
ብኖርም ባንኖርም
ምጽአት የሚጠብቅ በነፍስም በሥጋ።
ፍቅር አለኝ ላንተ
ምድር የሚሞላ፣
ከእግዜር የሚያስታርቅ ከእግዜር የሚያጣላ።
By Meron Ghetnet
@getem
@getem
@getem
❤39