#እዛ_ማዶ ጭስ ይጨሳል አጋፋሪ ይደግሳል
____________________________________
ማለት እስራኤል ከግብጽ ባርነት በወጡ ጊዜ በጭስ የተመሰለ ጉምና ደመና እየመራቸው ቅዱስ ሚካኤል መና እያወረደላቸው ስለወጡ ጭስ የተባለው የደመናው ምሳሌ ፤ አጋፋሪ የተባለው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡
#ያችን_ድግስ ውጬ ውጬ በድንክ አልጋ ተገልብጬ
____________________________________
ማለት በድግስ የተመሰለውን መና እስራኤል 40 ዘመን በአጋፋሪ በተመሰለው በቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እየተመገቡ በድንክ አልጋ የተመሰለችውን ኢየሩሳሌምን መውረሳቸውን የሚያመለክት ነው፡፡ “ያቺ ድንክ አልጋ ሆ አመለኛ ሆ ያለ አንድ ሰው ሆ አታስተኛ” ሆ” መባሉ እስራኤል ከግብጽ ሲወጡ 600,000 ሆነው ሲሆን ነገር ግን ሁሉም በምድረ በዳ አልቀው ኢየሩሳሌምን የወረሳት አንድ ኢያሱና አንድ ካሌብነው ለማለት ነው፡፡ #መልካም በዓል
____________________________________
ማለት እስራኤል ከግብጽ ባርነት በወጡ ጊዜ በጭስ የተመሰለ ጉምና ደመና እየመራቸው ቅዱስ ሚካኤል መና እያወረደላቸው ስለወጡ ጭስ የተባለው የደመናው ምሳሌ ፤ አጋፋሪ የተባለው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡
#ያችን_ድግስ ውጬ ውጬ በድንክ አልጋ ተገልብጬ
____________________________________
ማለት በድግስ የተመሰለውን መና እስራኤል 40 ዘመን በአጋፋሪ በተመሰለው በቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እየተመገቡ በድንክ አልጋ የተመሰለችውን ኢየሩሳሌምን መውረሳቸውን የሚያመለክት ነው፡፡ “ያቺ ድንክ አልጋ ሆ አመለኛ ሆ ያለ አንድ ሰው ሆ አታስተኛ” ሆ” መባሉ እስራኤል ከግብጽ ሲወጡ 600,000 ሆነው ሲሆን ነገር ግን ሁሉም በምድረ በዳ አልቀው ኢየሩሳሌምን የወረሳት አንድ ኢያሱና አንድ ካሌብነው ለማለት ነው፡፡ #መልካም በዓል