#እናንተኮ ገነትን እንዲ የጠላችዋት አስቀድማችሁም ስላሎደዳችዋት ነው ።አስቀድማችሁ በምድር ሳላችሁ ብትወዷት ኖሮ ዛሬ ባልሰለቻችሁ ነበር።
እንዴ አባ በምድር ሳለን ገነትን የት አገኝተናት ጠላና እሷ ያለችሁ እዚህ የት ተገናንተን አባ አል አንደኛው ንግግራቸው ድፍን ቅል ሆኖበት ያ ሰው ግን አብራቹ ነበረች እንጂ። ምድራዊቷ ቤተ ክርስቲያን ዕለት ዕለተ ታስቀድሱ ነበር ? ትቆርቡ ነበር?ማኅሌቷን ሰዓታቷን ትካፈሉ ነበር?
አይ አባ አልፎ አልፎ ግጥሚያና ትሬሊንግ ከሌላን እናስቀድሳለን በየ5ዓመቱም እንቆርባለን ሰዓታትም ቢሆን እግር ካደረሰን መቆሚያ ተደግፈን ጥቂት እንቆማለን።
#እሱንኮነው የምላችሁ እናንተ የሥጋ ትሬሊንግ እንጂ የመንፈስ ትሬሊንግ አድርጋችሁ አታውቁም በምድራዊቷ ገነት በቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ልምምዳችሁን በአግባቡ ስላልተለማመዳችሁ ሰማያዊቷ ገነት ሰለቸቻችሁ እናንተ ብቻ አይደላችሁም ብዙዎች በቤተመቅደሱ ሥርዓት ዝለው በሰማይ ገነት የሚበረቱ ይመስላቸዋል እንዲያ ግን አይደለም እግዚአብሔር ቸርነቱ በዝቶ ያለ ብዙ ትሩፋትና ድካም በየ ጥቂቱ ምሮ ሁሉንም ሰው ገነት ቢያስገባ እንኳን ከጥቂት ጊዜ በኋላ ብዙዎች ገነትን ይሰለቹና ካሎጣን ማለታቸው አይቀርም ምክንያቱም በምድር አልተለማመዷትምና ።
የዓለሙ ጫጫታና ውክቢያ አንዱን ቀራጭ ሌላውን ፈሪሳዊ አድርጎ እየጎተተ ያስቀረዋልና መልካም እንድትሆን በሚል ሰበብ የተሸከምከው በግ ውሻ ነው ጣለው እያሉ መልካሚቱን ቤተ ክርስቲያን ጥሎ ለሰማያዊቱ ገነት የተገባ ሆኖ እንዳይገኝም የልምዱን ጊዜ ከማያምኑ ጋር እንዲያጠፈ ይገደዳል ።በዚህ ዓይነት ታድያ ሦስት ሰዓት ቆሞ ማስቀደስ ጭንቅ የሚሆንበት እንዴት 24ሰዓት ከቅዱሳኑ ጋር ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ለማለት ይቻለዋል።
#እግዚአብሔርምኮ ጸጋ የሚሰጠው በጣሩበት በለፉበት በወጡበት በወረዱበት በዋሉበት እኮ ነው "..እንበለ ድካም ወጻሕማ ኢይትረከብ ጸጋ እግዚአብሔር..."ያለ ድካምና ልፋት የእግዚአብሔር ጸጋ እንዲሁ አትሰጥም እዲል መጽሐፉ። ገባችሁ እንዴ ልጆቼ ሲሉ ጠየቋቸው ሦስቱም በአውንታ አገታቸውን ነቀነቁ። ስለዚህ አሁን ምን አሰባችሁ በገነት መኖር ወይስ ከገነት መውጣት? ሁሉም በአንድላይ በዚህ መሆን ለኛ መልካም ነው የሚል ሀሳብ መጣላቸውና ካቀረቀሩበት ቀና ሲሉ እራሳቸውን ከምስጋናው ከተማ ከውዳሴ ሀገር ከመንበረ መንግሥት አገኙና መሰልቸት በማያገኘው መንፈስ ደስ እያላቸው ለምስጋና ገቡ።
..............ይቆየን።
አ.አ አበባ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መስከረም 1/1/2015 ዓ.ም
እንዴ አባ በምድር ሳለን ገነትን የት አገኝተናት ጠላና እሷ ያለችሁ እዚህ የት ተገናንተን አባ አል አንደኛው ንግግራቸው ድፍን ቅል ሆኖበት ያ ሰው ግን አብራቹ ነበረች እንጂ። ምድራዊቷ ቤተ ክርስቲያን ዕለት ዕለተ ታስቀድሱ ነበር ? ትቆርቡ ነበር?ማኅሌቷን ሰዓታቷን ትካፈሉ ነበር?
አይ አባ አልፎ አልፎ ግጥሚያና ትሬሊንግ ከሌላን እናስቀድሳለን በየ5ዓመቱም እንቆርባለን ሰዓታትም ቢሆን እግር ካደረሰን መቆሚያ ተደግፈን ጥቂት እንቆማለን።
#እሱንኮነው የምላችሁ እናንተ የሥጋ ትሬሊንግ እንጂ የመንፈስ ትሬሊንግ አድርጋችሁ አታውቁም በምድራዊቷ ገነት በቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ልምምዳችሁን በአግባቡ ስላልተለማመዳችሁ ሰማያዊቷ ገነት ሰለቸቻችሁ እናንተ ብቻ አይደላችሁም ብዙዎች በቤተመቅደሱ ሥርዓት ዝለው በሰማይ ገነት የሚበረቱ ይመስላቸዋል እንዲያ ግን አይደለም እግዚአብሔር ቸርነቱ በዝቶ ያለ ብዙ ትሩፋትና ድካም በየ ጥቂቱ ምሮ ሁሉንም ሰው ገነት ቢያስገባ እንኳን ከጥቂት ጊዜ በኋላ ብዙዎች ገነትን ይሰለቹና ካሎጣን ማለታቸው አይቀርም ምክንያቱም በምድር አልተለማመዷትምና ።
የዓለሙ ጫጫታና ውክቢያ አንዱን ቀራጭ ሌላውን ፈሪሳዊ አድርጎ እየጎተተ ያስቀረዋልና መልካም እንድትሆን በሚል ሰበብ የተሸከምከው በግ ውሻ ነው ጣለው እያሉ መልካሚቱን ቤተ ክርስቲያን ጥሎ ለሰማያዊቱ ገነት የተገባ ሆኖ እንዳይገኝም የልምዱን ጊዜ ከማያምኑ ጋር እንዲያጠፈ ይገደዳል ።በዚህ ዓይነት ታድያ ሦስት ሰዓት ቆሞ ማስቀደስ ጭንቅ የሚሆንበት እንዴት 24ሰዓት ከቅዱሳኑ ጋር ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ለማለት ይቻለዋል።
#እግዚአብሔርምኮ ጸጋ የሚሰጠው በጣሩበት በለፉበት በወጡበት በወረዱበት በዋሉበት እኮ ነው "..እንበለ ድካም ወጻሕማ ኢይትረከብ ጸጋ እግዚአብሔር..."ያለ ድካምና ልፋት የእግዚአብሔር ጸጋ እንዲሁ አትሰጥም እዲል መጽሐፉ። ገባችሁ እንዴ ልጆቼ ሲሉ ጠየቋቸው ሦስቱም በአውንታ አገታቸውን ነቀነቁ። ስለዚህ አሁን ምን አሰባችሁ በገነት መኖር ወይስ ከገነት መውጣት? ሁሉም በአንድላይ በዚህ መሆን ለኛ መልካም ነው የሚል ሀሳብ መጣላቸውና ካቀረቀሩበት ቀና ሲሉ እራሳቸውን ከምስጋናው ከተማ ከውዳሴ ሀገር ከመንበረ መንግሥት አገኙና መሰልቸት በማያገኘው መንፈስ ደስ እያላቸው ለምስጋና ገቡ።
..............ይቆየን።
አ.አ አበባ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መስከረም 1/1/2015 ዓ.ም