ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#መዋዕለ_ጾም

ጾመ ለተወሰነ ጊዜ ከመብልና መጠጥ ተከልክሎ መቆየት ነው፡፡ ለተወሰነ ጊዜ ከምግብ ተቆጥቦ መቆየት ለጤንነት ለሥጋም ለነፍስም ጠቀሜታ አለው፡፡

#ለምን_እንጾማለን?

በደካማ የሥጋ ፈቃድ ምክንያት ሕይወትን በሚዋጋ ሰይጣንና ከሱም ጋር በሚመጡ ፈተናዎች ላይ መንፈሳዊ ኃይልን ለማጠናከር የኃጢኣት ይቅርታና በረከት ለማግኘት ነው፡፡ ሐዋርያት ‹‹ጌታ ሆይ! ይህን ክፉ መንፈስ ልናወጣው ያልቻልነው ስለምንድነው?›› ብለው ጠየቁት ጌታም ‹‹ስለእምነታችሁ ደካማነት ነው……….. ይህ ዓይነት ግን ከጾምና ጸሎት በቀር አይወጣም›› ብሎ መለሰላቸው፡፡ ማቴ17÷21
በመልሱ ‹‹የዚህ ዓይነት›› የሚለው ኃይለ ቃል የጨለማ ኃይሎች የሚለውን ያመለክታል፡፡
‹‹ጦርነታችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለም፤ ከጨለማ ገዢዎች አለቆችና ሥልጣኖች ጋር›› ነው ብሎ ሐዋርያው እንደገለጠው፡፡ /ኤፌ6÷12/

#የጾም_ጥቅም?

የሥጋ ፈቃድ ለነፍስ ፈቃድ ለማስገዛት ይረዳል፤
ሰውነትን በእግዚአብሔር ዘንድ ታዛዥና ትሁት ያደርጋል፤
ታዛዥነትን ያሳያል፤
ለአካላዊ ብቃትና ጤንነትም አስተዋጽኦ አለው፤
ለሰውነት የምግብ መፍጫና ማዋሐጃ ክፍሎች የዕረፍት ጊዜ ያስገኛል፤

#በጾም_ወቅት_የሚወሰዱ_ጥንቃቄዎች

መጾም ከመብልና መጠጥ ብቻ አይደለም፡፡ ሰውን /ራስንም ጭምር/ ከሚጎዱ መጥፎ ነገሮች መታቀብ፣ የሰውነትን ክፍሎች ከጥፋት ሥራ መቆጣጠር ያስፈልጋል፡፡ ከምግብ እንደምንጾም ሁሉ ወደ ክፉ ተግባር ከሚገፋፉ ስሜቶች ሁሉ መከልከል ትልቅ ጾም ነው፡፡

ሌላው የበደሉትን ይቅርታ መጠየቅ የተበደሉትን ይቅር ማለት /መተው ይቅር መባባል ነው፡፡ ይቅር የማይሉ ይቅርታ የላቸውም፡፡ ይቅር አለመባባል ከእግዚአብሐየር ይቅርታ ራስን በፈቃድ ማግለል ነው፡፡

እምነታችን የፍጹምነት ሥራ የሚሰራው በሕይወታችን የምንወደውን ሁሉ አግኝተን ደስ ተሰኝተን ለመኖር ከፍ ብለን የጠቀስናቸው ሁሉ ተስተካክለውና ተሟልተው መጠበቅ ይኖርባቸዋል፡፡
የተሻለ ኑሮ ለመኖር አካሄዳችን ከእግዚአብሔር ጋር እናደርጋለን፡፡

ምንጭ መዝገበ ታሪክ
ክፍል ፩

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
#መዋዕለ_ጾም

ጾመ ለተወሰነ ጊዜ ከመብልና መጠጥ ተከልክሎ መቆየት ነው፡፡ ለተወሰነ ጊዜ ከምግብ ተቆጥቦ መቆየት ለጤንነት ለሥጋም ለነፍስም ጠቀሜታ አለው፡፡

#ለምን_እንጾማለን?

በደካማ የሥጋ ፈቃድ ምክንያት ሕይወትን በሚዋጋ ሰይጣንና ከሱም ጋር በሚመጡ ፈተናዎች ላይ መንፈሳዊ ኃይልን ለማጠናከር የኃጢኣት ይቅርታና በረከት ለማግኘት ነው፡፡ ሐዋርያት ‹‹ጌታ ሆይ! ይህን ክፉ መንፈስ ልናወጣው ያልቻልነው ስለምንድነው?›› ብለው ጠየቁት ጌታም ‹‹ስለእምነታችሁ ደካማነት ነው……….. ይህ ዓይነት ግን ከጾምና ጸሎት በቀር አይወጣም›› ብሎ መለሰላቸው፡፡ ማቴ17÷21
በመልሱ ‹‹የዚህ ዓይነት›› የሚለው ኃይለ ቃል የጨለማ ኃይሎች የሚለውን ያመለክታል፡፡
‹‹ጦርነታችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለም፤ ከጨለማ ገዢዎች አለቆችና ሥልጣኖች ጋር›› ነው ብሎ ሐዋርያው እንደገለጠው፡፡ /ኤፌ6÷12/

#የጾም_ጥቅም?

የሥጋ ፈቃድ ለነፍስ ፈቃድ ለማስገዛት ይረዳል፤
ሰውነትን በእግዚአብሔር ዘንድ ታዛዥና ትሁት ያደርጋል፤
ታዛዥነትን ያሳያል፤
ለአካላዊ ብቃትና ጤንነትም አስተዋጽኦ አለው፤
ለሰውነት የምግብ መፍጫና ማዋሐጃ ክፍሎች የዕረፍት ጊዜ ያስገኛል፤

#በጾም_ወቅት_የሚወሰዱ_ጥንቃቄዎች

መጾም ከመብልና መጠጥ ብቻ አይደለም፡፡ ሰውን /ራስንም ጭምር/ ከሚጎዱ መጥፎ ነገሮች መታቀብ፣ የሰውነትን ክፍሎች ከጥፋት ሥራ መቆጣጠር ያስፈልጋል፡፡ ከምግብ እንደምንጾም ሁሉ ወደ ክፉ ተግባር ከሚገፋፉ ስሜቶች ሁሉ መከልከል ትልቅ ጾም ነው፡፡

ሌላው የበደሉትን ይቅርታ መጠየቅ የተበደሉትን ይቅር ማለት /መተው ይቅር መባባል ነው፡፡ ይቅር የማይሉ ይቅርታ የላቸውም፡፡ ይቅር አለመባባል ከእግዚአብሐየር ይቅርታ ራስን በፈቃድ ማግለል ነው፡፡

እምነታችን የፍጹምነት ሥራ የሚሰራው በሕይወታችን የምንወደውን ሁሉ አግኝተን ደስ ተሰኝተን ለመኖር ከፍ ብለን የጠቀስናቸው ሁሉ ተስተካክለውና ተሟልተው መጠበቅ ይኖርባቸዋል፡፡
የተሻለ ኑሮ ለመኖር አካሄዳችን ከእግዚአብሔር ጋር እናደርጋለን፡፡

ምንጭ መዝገበ ታሪክ
ክፍል ፩

👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit