Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
የማይቀርበት የመጽሐፍ ምርቃት ኦርቶዶክሳውያ ሁላችሁ የካቲት 29 በዕለተ ቅዳሜ ከ 7:30 ጀምሮመርካቶ በሚገኘው ዳግሚት ደብረ ሊባኖስ ደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ገዳም እንዳይቀሩ በረከታቸው ይድረሰንና የብጹሕ አባታችን የአቡነ ሰላማ መታሰቢያም የሚሆኑ መርሐግብራት ስለተዘጋጁ ብጹሐን ጳጳሳትና መምህራን የመጽሐፉን ይዘት እና ፍሬ ነገር ትንታኔን ይሰጡበታልና ተጋብዘዋል !!!! 🙏🙏🙏
መጽሐፉን የሚፈልግ ሰው በዚህ ሊንክ ያናግሩኝ
@Redu21Da
መጽሐፉን የሚፈልግ ሰው በዚህ ሊንክ ያናግሩኝ
@Redu21Da
#ዛሬ የኪዳናት ሁሉ ፍጻሜ #ኪዳነ #ምሕረት ናት።ለቅዱሳኑ ለአዳም፣ለኖኅ፣ለመልከጼዲቅ፣ለአብር
ሃም፣ለዳዊት የተገባው ቃልኪዳን ሁሉ በእግዝእትነ ድንግል ማርያም ፍጻሜውን አገኘ።ይህ ኪዳነ እግዚአብሔር ምንድነው? ቢሉ የእግዚአብሔር ወልድ ሰው መሆን ነው።ሰው ሆኖም መዳናችንን መፈጸም ነው።
#ቅዱስ ዳዊት “ማዳን የእግዚአብሔር ነው፥ በረከትህም በሕዝብህ ላይ ነው።” መዝ 3፥8
ብሎ እንደተናገረው ሰውን ከተፈረደበት የሞት ፍርድ ማዳን የሚቻለው የፈረደበት እግዚአብሔር ነው።
#“ጽድቅንና ፍርድን ይወድዳል፤ የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ሞላች።”(መዝ 33፥5) በሚለው ቃልም ምን እግዚአብሔር ሰውን ማዳን(ጽድቅ) ቢችልም ፍርድንም ይወድዳል።ሰውን በቸርነቱ የማዳን ፈቃዱ ጽድቅ ሲሆን፤የበደለ ሰው ነውና ሊክስ የሚገባውም ሰው ነው፦ይህ ፍርድ ይባላል።
ሰው ደግሞ ራሱ የሞት ፍርድ ስላለበት ሰውን ማዳን የማይቻለው ነው።ታዲያ ምን ተሻለ? የሞት ፍርድ የሌለበት፤የባሕርይ ጉስቁልና (fallen nature)፤መርገመ አዳም መርገመ ሔዋን ያላገኘው ንጹሕና ቅዱስ ሰው ነዋ !!! ይህንን ነቢዩ ኢሳይያስ
“የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንነ እንደ ገሞራም በመሰልነ ነበር።”
(ኢሳ1፥9) በማለት የገለጸው ከላይ ካነሣናቸው ጉዳዮች የቀረች ንጹሕ ዘር ታስፈልግ ነበር።ከዚህች ንጹሕ ዘር ነው ራሱ እግዚአብሔር የነሣውን ሥጋዋን ነፍሷን ተዋሕዶ የሚያድነን።
#ይህቺ አዳምና ሔዋን በበደሉት በደል ከመጣው ጣጣ ሁሉ ከአዳም ልጆች በተለየ መልኩ ያስቀራት ዘር እመቤታችን ናት።ልብ በሉ "ዘርን ባያስቀርልን" አለ እንጂ "ዘሮችን" አላለም።ዘርዪቱ አንዲት ናት።ልዩ ናት!!!አትደገምም፤አትነገርም።ይህቺ ሰዎች ሁሉ ላይ ከመጣው የሞት ዕዳ የቀረች (የተረፈች) ዘር እመቤታችን ለመሆኗ ሰማያውያን መላእክትን ምድራውያን ጻድቃንን ምስክር እናቆማለን።“እግዚአብሔር ተናግሮአልና ሰማያት ስሙ፥ ምድርም አድምጪ።”(ኢሳ 1፥2)
1.“በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ሰኰናውን ትቀጠቅጣለህ።”
(ዘፍ 3፥15) የሰማዮች ሰማይ እግዚአብሔር የተናገረው ቃል ነው።ይህቺ ከእባቡ (ከሰይጣን) ጋር ጠላትነት ውስጥ የምትገባ ዘር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት።ሔዋን ከመሰለችህ ተሳስተሃል።ስለ እርሷማ ቅዱስ ኤፍሬም "ከይሲ ዲያቢሎስ ያሳታት ሔዋንን እግዚአብሔር ምጥሽንና ፃዕርሽን አበዛዋለሁ ብሎ ፈረደባት"ብሎ ተናገረ ።በምክረ ሰይጣን የተስማማ ሰው ከሰይጣን ጋር ጠላትነት ውስጥ ሊገባም አይችልም።ይህ የእመቤታችንና የሰይጣን ጠላትነት “ዘንዶውም በሴቲቱ ላይ ተቈጥቶ የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁትን የኢየሱስም ምስክር ያላቸውን ከዘርዋ የቀሩትን ሊዋጋ ሄደ”
(ራእይ 12፥17) ተብሎ ተጽፎለታል።ዘንዶው ማንነው? ካልክ “ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው፥ ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፤ ወደ ምድር ተጣለ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ።”(ራእይ 12፥9) በማለት የቀደመው እባብ (ሰይጣን) መሆኑን ቅዱስ ዮሐንስ ይነግርሃል።ሴቲቱስ?“ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።”ራእይ 12፥1
የተባላለት ድንግል ማርያም ናት።በዘፍጥረት በሴቲቱና በእባቡ ጠላትነት እንደሚደረግ እግዚአብሔር ነገረን።ቅዱስ ዮሐንስ ይህን ጠላትነት በተግባራዊ መልኩ በራእዩ አስረዳን።
2. “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።”(መዝ 45፥4) ልዑል እግዚአብሔር ማደሪያውን ለየ፤አመሰገነ፤አከበረ።
ቅዱስ እግዚአብሔር ማደሪያው የምትሆን ድንግል ማርያምን ከመርገመ አዳም ከመርገመ ሔዋን ጠበቀ ፤ በመጠበቁም አከበረ።
3.“ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ።”ሉቃ1፥27
ቅዱስ ገብርኤል የተላከው "ከደናግል ወደ አንዲቱ" አይደለም፤ወደ "አንዲት ድንግል" እንጂ!!!በሥጋ ደናግል የሆኑ ሴቶች ሊኖሩ ይችላሉ።እነዚህ ግን እንደ ማንኛውም የሰው ዘር መርገመ አዳም ወሔዋን ደርሶባቸዋል።እመቤታችን ግን ከዚህ ሁሉ ንጽሕት ናትና "አንዲት ድንግል" አላት።"አንዲት ድንግል" ማለትም "ብቸኛዪቱ ድንግል" ማለት ነው።ይህ ዓይነቱ ድንግልና ነው "የድንግልናሽ ምስጋናና ክብር ታላቅ ነው" ተብሎ የተመሰገነ።
4. “መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ፦ ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት።”(ሉቃ 1፥28)
ሰው ሁሉ ኃዘን አግኝቶት "ደስ ይበልሽ" የተባለች፤ሰው ሁሉ ከጸጋ እግዚአብሔር ጎድሎ "ጸጋ የሞላብሽ ሆይ" ተብላ የተመሰገነች፤በበደል በደሉንም ተከትሎ በደረሰብን መርገም ከእግዚአብሔር ተለይተን በነበርን ጊዜ መርገምም ሆነ በደል ካላገኛት ከእመቤታችን ጋር ጌታ እግዚአብሔር ነበር።ከሌሎች ሴቶች መካከል የተባረከች ናት እመቤታችን።መባረክ የመረገም ተቃራኒ መሆኑ ግልጥ ነው።ሌሎች ሴቶች ላይ “በፀነስሽ ጊዜ ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ፤ ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል፥ እርሱም ገዥሽ ይሆናል።” (ዘፍ 3፥16) የተባለው መርገም ሲደርስባቸው በእመቤታችን ግን ይህ ሁሉ የለባትም።
#በእውኑ #የእመቤታችን ሥጋ የወደቀው የአዳም ሥጋ እንዳልሆነ፤አዳም ሳይበድል የነበረው ሥጋ እንደሆነ ዐወቅን ተረዳን!!!ይህንን የገለጠልን ለእመቤታችን የምሕረት ቃል ኪዳን የሰጠ ቅዱስ እግዚአብሔር ስሙ ይክበር ይመስገን!!!
#የካቲት #ኪዳነ #ምሕረት /2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
ሃም፣ለዳዊት የተገባው ቃልኪዳን ሁሉ በእግዝእትነ ድንግል ማርያም ፍጻሜውን አገኘ።ይህ ኪዳነ እግዚአብሔር ምንድነው? ቢሉ የእግዚአብሔር ወልድ ሰው መሆን ነው።ሰው ሆኖም መዳናችንን መፈጸም ነው።
#ቅዱስ ዳዊት “ማዳን የእግዚአብሔር ነው፥ በረከትህም በሕዝብህ ላይ ነው።” መዝ 3፥8
ብሎ እንደተናገረው ሰውን ከተፈረደበት የሞት ፍርድ ማዳን የሚቻለው የፈረደበት እግዚአብሔር ነው።
#“ጽድቅንና ፍርድን ይወድዳል፤ የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ሞላች።”(መዝ 33፥5) በሚለው ቃልም ምን እግዚአብሔር ሰውን ማዳን(ጽድቅ) ቢችልም ፍርድንም ይወድዳል።ሰውን በቸርነቱ የማዳን ፈቃዱ ጽድቅ ሲሆን፤የበደለ ሰው ነውና ሊክስ የሚገባውም ሰው ነው፦ይህ ፍርድ ይባላል።
ሰው ደግሞ ራሱ የሞት ፍርድ ስላለበት ሰውን ማዳን የማይቻለው ነው።ታዲያ ምን ተሻለ? የሞት ፍርድ የሌለበት፤የባሕርይ ጉስቁልና (fallen nature)፤መርገመ አዳም መርገመ ሔዋን ያላገኘው ንጹሕና ቅዱስ ሰው ነዋ !!! ይህንን ነቢዩ ኢሳይያስ
“የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንነ እንደ ገሞራም በመሰልነ ነበር።”
(ኢሳ1፥9) በማለት የገለጸው ከላይ ካነሣናቸው ጉዳዮች የቀረች ንጹሕ ዘር ታስፈልግ ነበር።ከዚህች ንጹሕ ዘር ነው ራሱ እግዚአብሔር የነሣውን ሥጋዋን ነፍሷን ተዋሕዶ የሚያድነን።
#ይህቺ አዳምና ሔዋን በበደሉት በደል ከመጣው ጣጣ ሁሉ ከአዳም ልጆች በተለየ መልኩ ያስቀራት ዘር እመቤታችን ናት።ልብ በሉ "ዘርን ባያስቀርልን" አለ እንጂ "ዘሮችን" አላለም።ዘርዪቱ አንዲት ናት።ልዩ ናት!!!አትደገምም፤አትነገርም።ይህቺ ሰዎች ሁሉ ላይ ከመጣው የሞት ዕዳ የቀረች (የተረፈች) ዘር እመቤታችን ለመሆኗ ሰማያውያን መላእክትን ምድራውያን ጻድቃንን ምስክር እናቆማለን።“እግዚአብሔር ተናግሮአልና ሰማያት ስሙ፥ ምድርም አድምጪ።”(ኢሳ 1፥2)
1.“በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ሰኰናውን ትቀጠቅጣለህ።”
(ዘፍ 3፥15) የሰማዮች ሰማይ እግዚአብሔር የተናገረው ቃል ነው።ይህቺ ከእባቡ (ከሰይጣን) ጋር ጠላትነት ውስጥ የምትገባ ዘር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት።ሔዋን ከመሰለችህ ተሳስተሃል።ስለ እርሷማ ቅዱስ ኤፍሬም "ከይሲ ዲያቢሎስ ያሳታት ሔዋንን እግዚአብሔር ምጥሽንና ፃዕርሽን አበዛዋለሁ ብሎ ፈረደባት"ብሎ ተናገረ ።በምክረ ሰይጣን የተስማማ ሰው ከሰይጣን ጋር ጠላትነት ውስጥ ሊገባም አይችልም።ይህ የእመቤታችንና የሰይጣን ጠላትነት “ዘንዶውም በሴቲቱ ላይ ተቈጥቶ የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁትን የኢየሱስም ምስክር ያላቸውን ከዘርዋ የቀሩትን ሊዋጋ ሄደ”
(ራእይ 12፥17) ተብሎ ተጽፎለታል።ዘንዶው ማንነው? ካልክ “ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው፥ ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፤ ወደ ምድር ተጣለ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ።”(ራእይ 12፥9) በማለት የቀደመው እባብ (ሰይጣን) መሆኑን ቅዱስ ዮሐንስ ይነግርሃል።ሴቲቱስ?“ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።”ራእይ 12፥1
የተባላለት ድንግል ማርያም ናት።በዘፍጥረት በሴቲቱና በእባቡ ጠላትነት እንደሚደረግ እግዚአብሔር ነገረን።ቅዱስ ዮሐንስ ይህን ጠላትነት በተግባራዊ መልኩ በራእዩ አስረዳን።
2. “ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ።”(መዝ 45፥4) ልዑል እግዚአብሔር ማደሪያውን ለየ፤አመሰገነ፤አከበረ።
ቅዱስ እግዚአብሔር ማደሪያው የምትሆን ድንግል ማርያምን ከመርገመ አዳም ከመርገመ ሔዋን ጠበቀ ፤ በመጠበቁም አከበረ።
3.“ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ።”ሉቃ1፥27
ቅዱስ ገብርኤል የተላከው "ከደናግል ወደ አንዲቱ" አይደለም፤ወደ "አንዲት ድንግል" እንጂ!!!በሥጋ ደናግል የሆኑ ሴቶች ሊኖሩ ይችላሉ።እነዚህ ግን እንደ ማንኛውም የሰው ዘር መርገመ አዳም ወሔዋን ደርሶባቸዋል።እመቤታችን ግን ከዚህ ሁሉ ንጽሕት ናትና "አንዲት ድንግል" አላት።"አንዲት ድንግል" ማለትም "ብቸኛዪቱ ድንግል" ማለት ነው።ይህ ዓይነቱ ድንግልና ነው "የድንግልናሽ ምስጋናና ክብር ታላቅ ነው" ተብሎ የተመሰገነ።
4. “መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ፦ ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት።”(ሉቃ 1፥28)
ሰው ሁሉ ኃዘን አግኝቶት "ደስ ይበልሽ" የተባለች፤ሰው ሁሉ ከጸጋ እግዚአብሔር ጎድሎ "ጸጋ የሞላብሽ ሆይ" ተብላ የተመሰገነች፤በበደል በደሉንም ተከትሎ በደረሰብን መርገም ከእግዚአብሔር ተለይተን በነበርን ጊዜ መርገምም ሆነ በደል ካላገኛት ከእመቤታችን ጋር ጌታ እግዚአብሔር ነበር።ከሌሎች ሴቶች መካከል የተባረከች ናት እመቤታችን።መባረክ የመረገም ተቃራኒ መሆኑ ግልጥ ነው።ሌሎች ሴቶች ላይ “በፀነስሽ ጊዜ ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ፤ ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል፥ እርሱም ገዥሽ ይሆናል።” (ዘፍ 3፥16) የተባለው መርገም ሲደርስባቸው በእመቤታችን ግን ይህ ሁሉ የለባትም።
#በእውኑ #የእመቤታችን ሥጋ የወደቀው የአዳም ሥጋ እንዳልሆነ፤አዳም ሳይበድል የነበረው ሥጋ እንደሆነ ዐወቅን ተረዳን!!!ይህንን የገለጠልን ለእመቤታችን የምሕረት ቃል ኪዳን የሰጠ ቅዱስ እግዚአብሔር ስሙ ይክበር ይመስገን!!!
#የካቲት #ኪዳነ #ምሕረት /2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
የቀዳሚት ሰንበት መርሐግብርዎን ከአሁኑ በማስተካከል አብረውን ይሁኑ !🙏🙏🙏
“ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን #ቅዱሱን_የእግዚአብሔርን_መንፈስ አታሳዝኑ።”
| ኤፌሶን 4፥30
መቼም በዚህ በ ቲክ ታክ ዘመን እረጅምና ዝርዝር ጉዳዮችን መጻፍ እንደሞኝነት ሳይቆጠር አይቀርም ። አንድና ወጥነት ያለው ዘለግ ያለ ነገር ላይ ከመቆየት ይልቅ አጠር አጠር ያሉ ነገሮችን ለረጅም ጊዜ መከታተል የሚመረጥበት ወቅት ላይ ነን ስለዚህ ብዕሬን በአጭሩ ለማስታጠቅ እወዳለሁ።
#እግዚአብሔር_መንፈስ_ቅዱስ በየዋህቱ እርግብ ይመሰላል። እርግብ ቤት ሰርታ ከምትኖርበት ቦታዋ የፈለገ በደል ቢደርስባት ለቃ አትሄድም በድንጋይ ወርውረው ቢመቷት፣ እንቁላሎቿን ቢያፈርጡባት፣ ጫጭቶቿን ቢገሉባት ከመኖሪያዋ ጎጆ ወዴትም አትሄድም ። ሳይሰማት ሳያማት ሳይቆረቁራት ቀርቶ አይደለም የዋህ ስለሆነች ነው ። ነገር ግን ቤቷን መኖሪያዋን ያፈረሱባት እንደሆነ ላትመለስ እስከወዲያኛው ትሄዳለች።
መንፈሰ እግዚአብሔርም እንዲሁ ነው። #በአብ_በወልድ_በመንፈስ_ቅዱስ ስም አምነን አንድ ጊዜ በአርባና በሰማንያ ቀናችን ተጠምቀን ማደሪያ ቤቱ ካደረገን በኋላ መቼም መች ከኛ አይለይም። በአልዮ፣ በነቢብ ፣በገቢር ኃጢያት ብናሳዝ ነው ፤በምግባራችን ብናስከፋው ከቶ ከኛ አይርቅም። ነገር ግን አናውቅህም ብለን ከካድነው መቅደሱን ሰውነታችንን በክህደት ካፈረስንበት እንደ እርግቢቱ ጨርሶ ይለየናል።
ብዙዎች በራልን ተገለጠልን እያሉ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነውን በጥምቀት የከበረውን ቤተ ልቦናቸውን እያፈረሱ ከመንፈስ ቅዱስ ተለይተው ከፀጋ ተገፈው እንዲሁ ሲባዝኑ ማየት እየተለመደ መቷል። ድሮ ተናግረው አይደለም ገና ሳይናገሩ ሀሳባቸው የሚገባን ሳይቀልዱ የሚያስቁን በዐይናችን ፊት በሞገስ የሚገዝፉብን የጥበብ ሰዎች ዛሬ ግን ሁሉ ቀርቶ ብዙ አውርተው ጥቂቱ ንግግራቸው እንኳን የማይገባን ቀልደውልን ከማሳቅ ይልቅ የሚያናድዱን ግርማ ሞገሳቸው እርቆ ጥላ ቢስ የሆኑብን ብዙዎች እየመጡ ነው። ከነዚህ ሰዎች አንዱ አርቲስት #ሸዋፈራው_ደስአለኝ አንዱ ነው።
ሸዋን የወንዶች ጉዳይ ፣ ያረፈደ አራዳ ....ወዘተ በሚሉ ቆየት ባሉ ሥራዎቹ አስታውሰዋለው በጣም ከምወዳቸውና ከማከብራቸው ተዋንያን ግንባር ቀደሙ ነው ። ፌሽዋል ኤክስፕሬሽን የቃላት አጠቃቀም የድምጽ አወጣት ገጸ ባሕሪን መስሎ ሳይሆን ሆኖ የመጫወት ብቃት ያለው ባለ ግርማ ሞገስ ሙያተኛ ነበር ። ከጥቂት ግዝያት በኋላ ግን ያ ሁሉ ጠፍቶ ቀልዱ የማያምር ትወናው የሚያቅር ንግግሩም የሚያሳፍር እየሆነ መጣብኝ ምን እንደተፈጠረ በትክክል ባይገባኝም ዝም ብሎ ብቻ ከድሮው ቦታው እየወረደ እንደሆነ ይሰማኝ ነበር። ጌታን የተቀበለ ጴንጤ እንደሆነ ስሰማ ለዛ ይሆን ለዛውን የጣብኝ እያልኩ አስብ ነበር ፤ ከሰሞኑ ግን ከተራ ምዕመንነት አልፎ በፖስተር ደረጃ ሲሰብክ ሳይና ስሰማ ግን በእርግጥም የለዛ ቢስነቱ ምንጭ ከአርባ ቀኑ ማዕተብ ከቅዱሱ መንፈስ መለየቱ መሆኑ በእርግጥም ገባኝ።
አስቀድሜም እንዳልሁ አሁንም ደግሞ እላለሁ “ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን #ቅዱሱን_የእግዚአብሔርን_መንፈስ አታሳዝኑ።”
|ኤፌሶን 4፥30
አ.አ ኢትዮጲያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
የካቲት 27/2017 ዓ.ም
| ኤፌሶን 4፥30
መቼም በዚህ በ ቲክ ታክ ዘመን እረጅምና ዝርዝር ጉዳዮችን መጻፍ እንደሞኝነት ሳይቆጠር አይቀርም ። አንድና ወጥነት ያለው ዘለግ ያለ ነገር ላይ ከመቆየት ይልቅ አጠር አጠር ያሉ ነገሮችን ለረጅም ጊዜ መከታተል የሚመረጥበት ወቅት ላይ ነን ስለዚህ ብዕሬን በአጭሩ ለማስታጠቅ እወዳለሁ።
#እግዚአብሔር_መንፈስ_ቅዱስ በየዋህቱ እርግብ ይመሰላል። እርግብ ቤት ሰርታ ከምትኖርበት ቦታዋ የፈለገ በደል ቢደርስባት ለቃ አትሄድም በድንጋይ ወርውረው ቢመቷት፣ እንቁላሎቿን ቢያፈርጡባት፣ ጫጭቶቿን ቢገሉባት ከመኖሪያዋ ጎጆ ወዴትም አትሄድም ። ሳይሰማት ሳያማት ሳይቆረቁራት ቀርቶ አይደለም የዋህ ስለሆነች ነው ። ነገር ግን ቤቷን መኖሪያዋን ያፈረሱባት እንደሆነ ላትመለስ እስከወዲያኛው ትሄዳለች።
መንፈሰ እግዚአብሔርም እንዲሁ ነው። #በአብ_በወልድ_በመንፈስ_ቅዱስ ስም አምነን አንድ ጊዜ በአርባና በሰማንያ ቀናችን ተጠምቀን ማደሪያ ቤቱ ካደረገን በኋላ መቼም መች ከኛ አይለይም። በአልዮ፣ በነቢብ ፣በገቢር ኃጢያት ብናሳዝ ነው ፤በምግባራችን ብናስከፋው ከቶ ከኛ አይርቅም። ነገር ግን አናውቅህም ብለን ከካድነው መቅደሱን ሰውነታችንን በክህደት ካፈረስንበት እንደ እርግቢቱ ጨርሶ ይለየናል።
ብዙዎች በራልን ተገለጠልን እያሉ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሆነውን በጥምቀት የከበረውን ቤተ ልቦናቸውን እያፈረሱ ከመንፈስ ቅዱስ ተለይተው ከፀጋ ተገፈው እንዲሁ ሲባዝኑ ማየት እየተለመደ መቷል። ድሮ ተናግረው አይደለም ገና ሳይናገሩ ሀሳባቸው የሚገባን ሳይቀልዱ የሚያስቁን በዐይናችን ፊት በሞገስ የሚገዝፉብን የጥበብ ሰዎች ዛሬ ግን ሁሉ ቀርቶ ብዙ አውርተው ጥቂቱ ንግግራቸው እንኳን የማይገባን ቀልደውልን ከማሳቅ ይልቅ የሚያናድዱን ግርማ ሞገሳቸው እርቆ ጥላ ቢስ የሆኑብን ብዙዎች እየመጡ ነው። ከነዚህ ሰዎች አንዱ አርቲስት #ሸዋፈራው_ደስአለኝ አንዱ ነው።
ሸዋን የወንዶች ጉዳይ ፣ ያረፈደ አራዳ ....ወዘተ በሚሉ ቆየት ባሉ ሥራዎቹ አስታውሰዋለው በጣም ከምወዳቸውና ከማከብራቸው ተዋንያን ግንባር ቀደሙ ነው ። ፌሽዋል ኤክስፕሬሽን የቃላት አጠቃቀም የድምጽ አወጣት ገጸ ባሕሪን መስሎ ሳይሆን ሆኖ የመጫወት ብቃት ያለው ባለ ግርማ ሞገስ ሙያተኛ ነበር ። ከጥቂት ግዝያት በኋላ ግን ያ ሁሉ ጠፍቶ ቀልዱ የማያምር ትወናው የሚያቅር ንግግሩም የሚያሳፍር እየሆነ መጣብኝ ምን እንደተፈጠረ በትክክል ባይገባኝም ዝም ብሎ ብቻ ከድሮው ቦታው እየወረደ እንደሆነ ይሰማኝ ነበር። ጌታን የተቀበለ ጴንጤ እንደሆነ ስሰማ ለዛ ይሆን ለዛውን የጣብኝ እያልኩ አስብ ነበር ፤ ከሰሞኑ ግን ከተራ ምዕመንነት አልፎ በፖስተር ደረጃ ሲሰብክ ሳይና ስሰማ ግን በእርግጥም የለዛ ቢስነቱ ምንጭ ከአርባ ቀኑ ማዕተብ ከቅዱሱ መንፈስ መለየቱ መሆኑ በእርግጥም ገባኝ።
አስቀድሜም እንዳልሁ አሁንም ደግሞ እላለሁ “ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን #ቅዱሱን_የእግዚአብሔርን_መንፈስ አታሳዝኑ።”
|ኤፌሶን 4፥30
አ.አ ኢትዮጲያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
የካቲት 27/2017 ዓ.ም
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
Ethiopia: መቼ ነው ጌታ | ዘማሪ ዳዊት ክብሩ | Zemari Dawit Kibru | Mecha New Geta | New Orthodox Mezmur | መዝሙር
Ethiopia: መቼ ነው ጌታ | ዘማሪ ዳዊት ክብሩ | Zemari Dawit Kibru | Mecha New Geta | New Orthodox Mezmur | መዝሙር
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ቴሌግራም ቻናል
Telegram https://tttttt.me/Mikhadenagil
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ኢንስታግራም
Instagram https://www.instagram.com/mikhadenagil/?hl=en…
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ቴሌግራም ቻናል
Telegram https://tttttt.me/Mikhadenagil
የማኅበራችን የምክሐ ደናግል ማርያም ኢንስታግራም
Instagram https://www.instagram.com/mikhadenagil/?hl=en…
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
በቅርብ ቀን ይጠብቁን !🙏🙏🙏
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
Track 3- ሰው የለኝም አትበል🛑የንስሓ መዝሙራት ስብስብ🛑|| ለዐቢይ ጾም || collection || በልሳነ ሱራፊ ሚዲያ የተዘጋጀ @lisanesurafi
🛑የንስሓ መዝሙራት ስብስብ🛑
ዲያቆን ባስልዮስ ወንድሙ || ዲያቆን ኢዛና ማለፉ || ዲያቆን ታሪኩ ተስፋዬ || ዲያቆን በረከት ስለሺ
ዘማሪት አርሴማ ወ/አምላክ || ዘማሪት ፍሬ ሕይወት ልደቱ || ዘማሪት ጽዮን መኩሪያ || ዘማሪት ጸዳለ አማረ
በስብስቡ የተካተቱ መዝሙራት
Track 1- ጾምን ቀድሱ
https://youtu.be/TBhYsRf6fuM?si=wO5RuIo62rUXDjv7
Track 2- ለመልካም ኾነልኝ…
ዲያቆን ባስልዮስ ወንድሙ || ዲያቆን ኢዛና ማለፉ || ዲያቆን ታሪኩ ተስፋዬ || ዲያቆን በረከት ስለሺ
ዘማሪት አርሴማ ወ/አምላክ || ዘማሪት ፍሬ ሕይወት ልደቱ || ዘማሪት ጽዮን መኩሪያ || ዘማሪት ጸዳለ አማረ
በስብስቡ የተካተቱ መዝሙራት
Track 1- ጾምን ቀድሱ
https://youtu.be/TBhYsRf6fuM?si=wO5RuIo62rUXDjv7
Track 2- ለመልካም ኾነልኝ…
#ምስጋና ቢስ ጤና
----------------------------
በሽታውን ለምዶ ለኖረ በጠና
መዳን መታመም ነው መቆየት በጤና
ሕመመ ለምዶ ለምዶ
እኸኸን ለምዶ ለምዶ
ወንጀል ይመስለዋል የዳነ ተገዶ
ከለመደው ሕመመ ካከረመው በደል
ማንም ቢነጣጠል ጸናበት ነው እንጂ
ተፈወሰ አትበል
ጤና ለራቀው ሰው ሕመም ነው ጤንነት
ከለመደው መኖር እኸኸ ከሚልበት
አለመታመም ነው የሱ መጻጉነት
ስለዚህ ወዳጄ
ማዳንን ስለቻልክ መፈወስ ስላወክ
ልፈውስ አትበለው ሕመሙን አርቀህ ጤናውን እያወክ
ያ ደጉ ጌታ እንኳ ለማዳን የመጣው
ልድን ተወዳለህ? ብሎ ያስፈቀደው
ላንዳንዱ በሽታው
ጤናው እንደሆነ አስቀድሞ አውቆ ነው
መዳን ጤና የሚሆን ላንዳንዱ ብቻ ነው
ጤናው ጤና ነስቶት በሽታ የሆነበት
ኁልቁ ሰው አለልህ ለቁጥር የሚያዳግት
ያዳነውን መድኅን ሽቅብ የሚያንጓጥጥ
ያዳነኝ ያ ሰው ነው ብሎ የጠቆመው
መድኅኑን በሰው ፊት ኮንኖ ያቆመው
ተኝቶኮ አይደለም በአልጋ ቁራኛ
መጻጉዕ ድኖ ነው የሆነ ሕመምተኛ
እናማ የታመምክም ብትሆ በአልጋ የወደክ
ጤናህን በማጣት በጅጉ የደከምክ
አታማር ግድ የለም
ያንተ ጤንነትህ በደዌክ ውስጥ ነው
መናልባት ሕመም ቀና ያልክ ቀን ነው
#ማስታወሻነቱ :- በደዌ ደኛ በአልጋ ቁራኛ ለተያዙ ሁሉ ይሁንልኝ!
#የምሕረት-እናት-ድንግል-ማርያም ምሕረቱን ትላክላችሁ:: የወይን ጠጅ አኮ የላቸውም ብሎ አዲስ የወይን ጠጅ ባሰጠ አንደበቷ ዛሬም ጤናኮ የላቸውም ብላ ከቀድሞው የበለጠ አዲሰ ጤናን ታሰጣችሁ ታሰጠን! አሜን!
አ.አ ኢትዮጵያ
ከተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
መጋቢት ፲ ፫ ቀን ፳ ፻ ፲ ፬ ዓ.ም ጥንተ ጽሕፈቱ
----------------------------
በሽታውን ለምዶ ለኖረ በጠና
መዳን መታመም ነው መቆየት በጤና
ሕመመ ለምዶ ለምዶ
እኸኸን ለምዶ ለምዶ
ወንጀል ይመስለዋል የዳነ ተገዶ
ከለመደው ሕመመ ካከረመው በደል
ማንም ቢነጣጠል ጸናበት ነው እንጂ
ተፈወሰ አትበል
ጤና ለራቀው ሰው ሕመም ነው ጤንነት
ከለመደው መኖር እኸኸ ከሚልበት
አለመታመም ነው የሱ መጻጉነት
ስለዚህ ወዳጄ
ማዳንን ስለቻልክ መፈወስ ስላወክ
ልፈውስ አትበለው ሕመሙን አርቀህ ጤናውን እያወክ
ያ ደጉ ጌታ እንኳ ለማዳን የመጣው
ልድን ተወዳለህ? ብሎ ያስፈቀደው
ላንዳንዱ በሽታው
ጤናው እንደሆነ አስቀድሞ አውቆ ነው
መዳን ጤና የሚሆን ላንዳንዱ ብቻ ነው
ጤናው ጤና ነስቶት በሽታ የሆነበት
ኁልቁ ሰው አለልህ ለቁጥር የሚያዳግት
ያዳነውን መድኅን ሽቅብ የሚያንጓጥጥ
ያዳነኝ ያ ሰው ነው ብሎ የጠቆመው
መድኅኑን በሰው ፊት ኮንኖ ያቆመው
ተኝቶኮ አይደለም በአልጋ ቁራኛ
መጻጉዕ ድኖ ነው የሆነ ሕመምተኛ
እናማ የታመምክም ብትሆ በአልጋ የወደክ
ጤናህን በማጣት በጅጉ የደከምክ
አታማር ግድ የለም
ያንተ ጤንነትህ በደዌክ ውስጥ ነው
መናልባት ሕመም ቀና ያልክ ቀን ነው
#ማስታወሻነቱ :- በደዌ ደኛ በአልጋ ቁራኛ ለተያዙ ሁሉ ይሁንልኝ!
#የምሕረት-እናት-ድንግል-ማርያም ምሕረቱን ትላክላችሁ:: የወይን ጠጅ አኮ የላቸውም ብሎ አዲስ የወይን ጠጅ ባሰጠ አንደበቷ ዛሬም ጤናኮ የላቸውም ብላ ከቀድሞው የበለጠ አዲሰ ጤናን ታሰጣችሁ ታሰጠን! አሜን!
አ.አ ኢትዮጵያ
ከተክለ ኤል ኃይለ ማርያም
መጋቢት ፲ ፫ ቀን ፳ ፻ ፲ ፬ ዓ.ም ጥንተ ጽሕፈቱ
Forwarded from የዘማሪ ዳዊት ክብሩ Zemari Dawit Kibru Official Telegram Channel (Dawit Kibru)
YouTube
🔴አዲስ ዝማሬ🔴ሰው ያጣ(መጻጉዕ) ዘማሪት ሲስተር #ሕይወት ተፈሪ እና ዘማሪት መቅደላዊት በላቸው#ናና አማኑኤል@AbiStudio117
This is an Ethiopian Orthodox Church song which tells about the 4th Sunday of Abiy fasting. On this day the Church has preached our Lord Jesus had cured many people who had infirmity.