ዐውደ ምሕረት
3.67K subscribers
932 photos
24 videos
271 files
195 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
#መልከአ_ተክለሃይማኖት
#ሰላም_ለአክናፊከ
በቀኝ ጉንህ ሦስት በግራ ጉንህ ሦስት ሆነው ለሠረፁት ፮ቱ አክናፎችህ ሰላም እላለሁ
#ቅዱሱ_አባት_ሆይ
እኔ ልጅህ የአንተን በረከት እፈልጋለሁና የቀን ጉዳይ ጥሎኝ ለእርዳታ በምፈልግህ ጊዜ በነዚያ በክንፎችህ ፈጥነህ ድረስልኝ ።
MD | የእርዳታ ጥሪ ቀሲስ ፍስሐ አስማረ

1000587474208 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
171101103480311 አባይ ባንክ
163933217 በአቢሲንያ ባንክ

የሂሳብ ቁጥር ስም :- ፍስሐ አስማረ ዘለቀ / ፋንቱ ምህረቴ

በአሁኑ ወቅት ባደረባቸው የአንጀት ካንሰር በሽታ እየተሰቃዩ ሲሆን ይህንንም በሽታ በከፍተኛ ሕክምና ለመከታተል እስከ ብር 3,000,000 /ሦስት ሚሊየን ብር/ ገንዘብ ያስፈልጋቸዋል

የደብራችን መደበኛ አገልጋይ የሆኑት ቀሲስ ፍስሐ አስማረ በደብሩ በጊዜያዊነት ከነሐሴ 3 ቀን 1992 ዓ.ም ጀምሮ ከተቀጠሩ በኋላ ያላቸው የሥራ ትጋት ታይቶ ከግንቦት 11 ቀን 1993 ዓ.ም ጀምሮ በቋሚነት በዲቁና እና በተለያዩ የሥራ መደቦች ላይ ተመድበው በማገልገል ላይ እያሉ ባላቸው ብቁ የቤተ ክርስቲያን ሙያ ከህዳር ወር 2006 ዓ.ም ጀምሮ በሊቀ ዲቁና ኃላፊነት የሥራ መደብ ሲያገለግሉ ቆይተው ከህዳር ወር 2012 ዓ.ም ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ በቅስና የሥራ መደብ ተመድበው በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡

ቀሲስ ፍስሐ አስማረ በቅስና ሥራ ብቻ ሳይወሰኑ በማህሌት አገልግሎትም ብቁ ችሎታ ያላቸው በመሆኑ ሰፊ አገልግሎት የሚሰጡ ወንድም ሲሆኑ በአሁኑ ወቅት ባደረባቸው የአንጀት ካንሰር በሽታ እየተሰቃዩ ሲሆን ይህንንም በሽታ በከፍተኛ ሕክምና ለመከታተል እስከ ብር 3,000,000 /ሦስት ሚሊየን ብር/ ገንዘብ ያስፈልጋቸዋል
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እንኳን አደረሰን #ተመስገን
Forwarded from Ab 1st Sam 7:12
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በቅርብ ቀን

ይጠብቁን

ከመምህር ቢትወደድ ወርቁ !!!
ገበያ ላይ ውላሏል እኛ ደርሶናል እናንተስ ?


ኑ እና መርካቶ የሚገኘው ደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ቤ/ክርስቲያን ሲደርሱ በዚህ ስልክ
☎️ 0911003590 📞 ይደውሉ መጽሐፉን ያገኙታል እንዳያመልጥዎ 🕞🕞🕞⌛️
#አንዳንድ ልጆች ከወላጆቻቸው የሚበልጡበት ጊዜ አለ አንዳንድ ወላጆች ደግሞ በነገሮች ዕይታ ከልጆቻቸው የሚያንሱበትም ጊዜ አለ ። እናታችን ቅድስት ኢየሉጣ ይህን በመገንዘቧ ነበር ልጇን ሕፃኑ ቂርቆስን ስለ መልካም ምክሩ ልጇ ሆኖ ሳለ አባቴ ብላ ለመጥራት የተገደደችሁ ።
በእርግጥም የሥጋ ሞት እጅግ መራራና አስፈሪ ነው ። መድኅን ዓለም ክርስቶስ እንኳን ወዶ ፣ፈቅዶ የሞታችንን ጽዋ ሊጠጣልን ለካሳ፣ ለቤዛ መጥቶ ሳለ ጊዜው ደርሶ በአሙስ ምሽት የአይሁድ ወታደሮች ሊይዙት ሲመጡ ግን በአትክልት ቦታ በጌቴ ሰማኔ ሆኖ "አባት ሆይ ብትወድስ ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ " ሲል ጸሎትን አድርጓል። #ማቴ 26÷39
#ይህም የሚያሳየን በመከራችን ጊዜ ወደ ሰማይ አባታችን መጸለይ እንደሚገባን ብቻ ሳይሆን የሥጋ ሞት ምነኛ አሰቃቂ ና አስፈሪ እንደሆነ ጭምር የሚያሳይ ነው ። ስለሆነም የቅድስት እየሉጣ ፍርሃት አያስደንቅም የሚያስደንቀውስ የልጇ እሳት መድፈር ነው ። “ አባት ሆይ፥ ይህን ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ለሕፃናት ስለ ገለጥህላቸው አመሰግናለሁ፤ አዎን አባት ሆይ፥ ፈቃድህ በፊትህ እንዲህ ሆኖአልና።” #ሉቃስ 10፥21
በቤተክርስቲያናችን ታሪክ ገና በአፍላ ዕድሜያቸው በበሳልነታቸውና በአስተሳሰብ አድማሳቸው የተነሳ አረጋዊ ወይም ሽማግሌ ተብለው የተጠሩ ቅዱሳን አሉ ለምሳሌ ወደ ሀገራችን ከመጡ ከዘጠኑ ቅዱሳን መካከል ሮማዊው ኮከብ ዘሚካኤል(አቡነ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞ) ማንሳት ይቻላል:: ዘሚካኤል አረጋዊ የሚል ስያሜን ያገኙት ገና አስራ አምስት ዓመት እንኳን ሳይሞላቸው ነበር።
#ቅዱስ_ወንጌል ከአንዱ ከተማ ቢያሳድዷችሁ ወደ ሌላይቱ ከተማ ሽሹ እንዳለ ከሮም መኮንን ሸሽታ ወደ ሌላ ሀገር ልጇን ይዛ ብትሄድ ያን የሸሸችሁ ክፉ መኮንን በዚህም ሀገር አገኛት የምታመልከውን አምላክ ክዳ የእርሱን ጣዖት እድታመልክም ጠየቃት ቅድስት ኢየሉጣ ግን ከእግዚአብሔር በቀር ሌሎች አማልክትን ማምለክ የሚገባ ወይም የማይገባ መሆኑን ይህን የሦስት ዓመት ልጄን ጠይቀው እርሱ ይንገርህ አለችሁ
መኮንኑም ቅዱስ ቂርቆስን በተመለከተው ጊዜ ፊቱ ብሩህና ደስተኛ ሕፃን እንደሆነ አስተዋለ ቀርቦም አንተ ደስተኛ ሕፃን እንዴት ነህ ሲል የማግባባት ሰላምታን አቀረበለት ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን አዎን የኔ ደስታ ተጠብቆልኛል አንተ ግን ከዚህ እኩይ ሥራህ ካልተመለስ ልቅሶና ጥርስ ማፏጨት ጥልቅ ሐዘንም ይቆይሃል መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላና ደስታ የላቸውም ይላልና አለው።“ለክፉዎች ሰላም የላቸውም ይላል አምላኬ።” #ኢሳ 57፥21
#መኳንንቱንና ጣዖታቱንም ሁሉ እረገማቸው ከኃይሉም ጽናት የተነሳ ሁሉ አደነቁ እግዚአብሔር ንግግርንና ኃይልን ሰጥቶታልና "ስለ እኔ ወደ ገዥዎች ወደ ነገሥታትም ትወሰዳላችሁ ። አሳልፈውም ሲሰጡአችሁ፥ የምትናገሩት በዚያች ሰዓት ይሰጣችኋልና እንዴት ወይስ ምን እንድትናገሩ አትጨነቁ፤ በእናንተ የሚናገር የአባታችሁ መንፈስ ነው እንጂ፥ የምትናገሩ እናንተ አይደላችሁምና። ተብሎ እንደተጻፈ #ማቴ 10÷18-20
መኮንኑም የሕፃኑን ንግግር በሰማ ጊዜ አፈረ ታላቅ የውኃ ጋን አዘጋጅታችሁ ውኃው እስከሚፍለቀለቅ በእሳት ላይ ጣዱት ውኃውም ሲፈላ ሕፃኑንና እናቱን በዚያ ጨምሯቸው ብሎ አዘዘ ።
#ጭፍሮችም እንደተባሉት አደረጉ የውኃው ፍላትም ድምጹ እንደ ክረምት ጊዜ ነጎድጓድ የሚያስፈራና የሚያስገመግም ሆነ ይህ ጊዜ የሕፃኑ እናት ቅድስት ኢየሉጣ ፈራች ሃይማኖቷም ከልቧ ተሸረሸረ ልጄ ሆይ ይህ ነገር ይቅርብን ንጉሥ ያለንን እንፈጽም አለችው።
ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን ወደ ሰማይ አንጋጦ መላእክትን በጽረ አርያም ፣ ሐዋርያትን በስብከተ ዓለም ፣ ጻድቃንን በገዳም፣ ሰማዕታትን በደም ያጸናህ እናቴንም በሃይማኖት አጽናት ሲል ስለ እናቱ የእምነት መጉደል ወደ ፈጣሪው ጸለየ።
#እግዚአብሔርም የእናቱን ዐይነ ልቡና ገልጦ ለቅዱሳን ሰማዕታቱ ያዘጋጀውን የጽድቅ አክሊልን አሳያት ያን ጊዜ ቅድስት እየሉጣ በመንፈስ ተጽናናች ፣ በሃይማኖት ጸናች ንጉሡንና ጣዖታቱን ናቀች ልጇ ቂርቆስንም " #ልጄ_ስትሆን_አባት_ሆንክኝ " አለችሁ ተያይዘውም በእሳት ወደ ተፍለቀለቀው የውኃ ጋን ውስጥ ገቡ
#ከእግዚአብሔር_የተላከ_የመላእክት_አለቃ_ቅዱስ ገብርኤልም ከዐይን ጥቅሻ ፈጥኖ መጥቶ #በጌታችን_በመድኃኒታችን_በኢየሱስ_ክርስቶስ_መስቀል ያን ፍል ውኃ እንደ ክረምት ጊዜ ውርጭ አቀዘቀዘው። ሕፃኑና እናቱም ያለ ምንም ጉዳት ከጋኑ ወጡ። " #የእግዚአብሔር_መላእክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል " እንዲል #መዝ 33÷7
.......... #ይቆየን............
#የእግዚአብሔር ቸርነት የመላእኩ ጠባቂየት የቅዱሳኑ የእናትና ልጅ በረከታቸው አይለየን !

አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ሐምሌ ፲ ፰/፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
+++ ታቦትና ጣዖት አንድ ሆነው አያውቁም።+++

ይልቁንም ታቦተ ጽዮን ዳጎንን (ጣዖተ ፍልስጥኤምን) ስትገለብጥና ስትቆራርጥ አንብበናል። (1ሳሙ 5:3)

ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን "ኦሪታዊት ናት" ስትል ትቆይና መልሰህ ደግሞ "ታቦቱ ለምን የኦሪቱን አልመሰለም?" ብለህ ትሟገታለህ። የአዲስ ኪዳኑ መሥዋዕት በቤተክርስቲያን የምንቀበለው (የምንበላው የምንጠጣው) ክርስቶስ ከኦሪቱ መሥዋዕት ፍፁም የተለየ እንደሆነ እንዲሁ የአዲስ ኪዳኑም መሠዊያ ከኦሪቱ ልዩ ነው። "መሠዊያ አለን።" እንዲል ሐዋርያው። (ዕብ 13:10) ያ መሠዊያ ምንድነው? ያልክ እንደሆነ የሐዲስ ኪዳን መሥዋዕት የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም ምእመናን ይበሉትና ይጠጡት ዘንድ የሚቀርብበት የአዲስ ኪዳን ታቦት ነው።

"ታቦት ለምን በዛ?" ይልሃል ደግሞ በዚያ በኩል፤ መልሳችን አጭር ነው። በብሉይ ኪዳን ቤተ መቅደሱ አንድ ብቻ እርሱም የሰሎሞን ቤተ መቅደስ አልነበረምን? በሐዲስ ኪዳን ግን ክርስትናው በዓለም ናኝቷልና ክርስቲያኖች በበቀሉበት ሥፍራ ሁሉ ይሠራል እንጂ "ለምን ቤተ መቅደስ በዛ?" አይባልም።

ሥልጣነ ክህነትስ ለአንዱ ነገድ ለነገደ ሌዊ ብቻ ይሰጥ የነበረ አልነበረምን? በሐዲስ ኪዳን ግን ነገር ተለውጦ በክህነቱ ለማገልገል ብቁ ለሆኑና መንፈሳዊውን መስፈርት ለሚያሙሉ አማኞች ይሰጣል። "ለምን ለሁሉ ይሰጣል?" አይባልም! (1ጢሞ 3:1-13፣ ቲቶ 1:7)

ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ በአዲስ ኪዳን “በሰማይም ያለው የእግዚአብሔር መቅደስ ተከፈተ፥ የኪዳኑም ታቦት በመቅደሱ ታየ፥ መብረቅና ድምፅም ነጐድጓድም የምድርም መናወጥ ታላቅም በረዶ ሆነ።” (ራእ 11፥19) በማለት ይነግረናል። ይህ ሲጠቀስለት ደግሞ በአንድምታ ትርጓሜ ያምን ይመስል "ይህ አገላለጽ Symbolic እንጂ ስለ ታቦቱ አይደለም።" ይላል።

፩. ታቦት ጣዖት ከሆነ እንዴት በሰማይ ሊኖር ቻለ?

፪. "Symbolic ወይም ምሳሌያዊ ነው።" ብትሉ እንኳን በሰማያዊት ኢየሩሳሌም ያለ መልካም ነገር እንዴት በጣዖት Symbolic ሆኖ ሊገለጥ ይችላል?

በኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያንም ይህች ታቦት:- ታቦት ዘዶር እንደምትባልና ምሳሌነቷም ለአማናዊቷ ታቦት ለድንግል ማርያም መሆኑን መምህራን ያስተምራሉ። የራሱን ሰውነት በመቅደስ መስሎ ስለ ተናገረ ጌታ ትንሣኤ ትንቢት የተናገረ ክቡር ዳዊት "አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦት" ብሎ ትንቢት መናገሩን ልብ እንበል። (መዝ 131:8) የመቅደሱ (የእርሱ) ታቦት (ማደርያው) እናቱ ድንግል አይደለችምን? ለክርስቶስ ማደርያነት በዚህ መንገድ የቀረበ ታቦትን እንዴት ጣኦት ትላለህ?

የምድሩ ታቦት ነገር ሲነገረው የማይገባው ስለ ሰማዩ ታቦት ቢነገረው እንዴት ይቀበል ይሆን?

እኛስ የታቦት ሥራ አለብን!!


መምህር ቢትወደድ ወርቁ