#ዝክረ_ቅዱሳን
°°°°°°_
#ቅዱስ_እስትንፋሰ_ክርስቶስ
-----------------------------------------
#አዘጋጅ ና አቅራቢ :- #ዲ/ን ሙሉ ዓለም አየለ
#የጊዜ ርዝማኔ 10 ደቂቃ 25 ሰከንድ
መጠን 11.9 mb ብቻ
#ዐውደ_ምሕረት_የእናንተ!
°°°°°°_
#ቅዱስ_እስትንፋሰ_ክርስቶስ
-----------------------------------------
#አዘጋጅ ና አቅራቢ :- #ዲ/ን ሙሉ ዓለም አየለ
#የጊዜ ርዝማኔ 10 ደቂቃ 25 ሰከንድ
መጠን 11.9 mb ብቻ
#ዐውደ_ምሕረት_የእናንተ!
“የጽዮን ልጅ ሆይ አትፍሪ እነሆ ንጉሥሽ በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ይመጣል"የተባለው ተፈፀመ
ት.ዘካ 9÷9
ይህ በነቢዩ ዘካሪያስ አስቀድሞ በትንቢት የተነገረ አማናዊ ቃል የተፈፀመው በኢየሩሳሌም ከተማ ደብረ ዘይት አቅራቢያ ቤተ ፋጌ በምትባል መንደር ነው::ጊዜው በግምት 2000ዓመት ገደማ ይሆናል::ከተማዋ በደስታ ታምሳለች የኢየሩሳሌም ከተማ በተለያዮ ጊዜያት ልዮ ልዮ ነገስታት በሰረገላ ተቀምጠው ጎብኝተዋታልች፣ገስተዋታል የዛሬው ግን ልዮ ንጉሥ ነው ስለ ፍቅር ሲል የእሳት ሰረገላውን ትቶ አህያን የመረጠ አበ ትህትና(የትህትና አባት)መድኃኒት የሆነ ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው::ሕዝቡም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመምጣት ላይ እንዳለ ሲያውቅ ሊቀበለው ወጣ አጠገቡም ሲደርሱ ልብሳቸውን በአህያዪቱ ውርንጭላ ላይ አንጥፈው አስቀመጡት፡፡ አንዳንዶች ያልፍበት በነበረ መንገድ ልብሳቸውን እንዳንዶቹ ደግሞ የዘንባበ ዝንጣፊ ያነጥፉ ነበር፡፡ማቴ 21÷1-17 ከፊትና በኋላ ያሉት ብዙ ሰዎችም “ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ! በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው! ሆሳዕና በአርያም!” እያሉ ይጮኹ ነበር።
ሆሳዕና ማለት መድኃኒት ማለት ነው ሕዝቡም እንዲ ማለታቸው አቤቱ አሁን አድን ብሎ መዝሙረኛው ዳዊት የተናገረውን ንግግር ሲገልጡ ነው ።አህያይቱ ተሰርቃ ከነ ልጆ ከነ(ውርንጭላዋ) ታሰረች ነበር ያሰራት ሰው ሌባ ነወ የሌላ ሰው ንብረት እንደ ንብረቱ አድርጎ ከደጃፉ አስሯታልና ሌባው በቤቱ ያቆያት 5ቀን ተኩል ነው" የማታ የማታ እውነት ይረታ" እንዲሉ አበው እውተኛ ፈራጅ በወጣ ጊዜ አህያዋ ከእስራቷ እንድትፈታ አደረገ ::አህያዋ ና ውርንጫላዋ አዳምና ልጆቹ ሲሆኑ ሌባው ዲያቢሎስ ነው: በአሰት ንግግር እግዚአብሔርን ከመሰለ አምላክ ገነት ከምታክል ቦታ ለይቶ ለ5ቀን ተኩልያክል ጊዜ በሲዖል አስሮናል::
5500 ዘመን ሙሉ በእግረ አጋንንት ተይዘን ሰንጨነቅ መድኃኒት ከሆነው ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ማንም አልደረሰልንም ነበርና ስለዚህ በደስታ ተሞልተው የሆሳዕና አሉ ::
ለምን በአህያና በአህያ ወርንጭላ ላይ ተቀመጠ ቢሉ?
✝እናቲቱ አህያ የብሎይ ውርንጭላይቱ የአዲስ ኪዳን ምሳሌ ናቸው በሁለቱ መቀመጡ ኦሪትን እንዳልሻረ ወንጌልንም እንደሰጠ ሲያጠይቅ አንድም እናቲቱ አህያ ሸክም የለመደች ነች አዲሲቱ ውርንጫይቱ ግን ሽክም ያለመደች የቤተ አሕዛብና የቤተ እስራኤል ምሳሌ ናቸው::ኦሪት ከባድ ወንጌል ግን ቀሊል ናትና አንድም ሕግ የለመዱና ሕግ ያለመዱ እዝቦች ናቸውና:: አንድም አህያ በወለደችሁ ታርፋለች እንዲሉ ኦሪትም በወንጌል ታግዛ ጸንታለችና ነው::ሌላው
👉ፋረስና በቅሎ ለጦርነት ይሁላሉ አህያ ግን አትውልም ጥንት ነቢያት ክፉ ትንቢትና ክፎ ወሬ ይዘው ሲመጡ ማቅ ለብሰው ትቢያ ነስንሰው በፈረስ ወይም በበቅሎ ተቀምጠው ወደ ከተማ ይባሉ መልካም ዜናና ትንቢት ይዘው የመጡ እንደሆነ ደግሞ በአህያ ላይ ተቀምጠው ይመጣሉ ሕዝቡም መቀመጫቸውን አይቶ መልካም ዜና እንዳመጡ ተረድቶ በደስታ ይበቀላቸው ነበርና ጌታችንም መልካም የድኅነት ዜና ሆኜ መጣው ሲል ከቤተ ፋጌ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ በአህያ ላይ ተቀመጠ::
👉በአህያ ተቀምጦ እንደሚመጣ በኦሪት የተነገሩ የኢሳይያስና የዘካሪያስን ትንቢት' ለመፈጸም ነው::(ትንቢቱን ለመፈጸም) ዘካ9÷9
👉ከእኔ ተማሩ እኔ የዋህ በልቤም ትሁት ነኝና እንዳለ ትዕትናን ለማስተማር ማንንም አትናቁ ሲል ማቴ11÷29 ዮሐ13÷1
👉በፈረስና በበቅሎ ያለን ሰው ማንም አይደርስበትም በአህያ ያለን ሰው ግን በቶሎ ይደርሱበታል ስለዚህ እኔ የቅርብ አምላክ ነኝ እንጂ የእሩቅ አምላክ አይደለሁም ከፈለጋችሁን በቅርብ ታገኙኛላችሁ ለማለት በአህያ ተቀመጠ ኤር 23÷23
🌴ሕዝቡ የዘንባባ ዝንጣፊ መያዛቸው🌴
🌿- ይስሐቅ በተወለደ ጊዜ አብርሃም ደስ ብሎት ዘንባባ ይዞ እግዚአብሔርን አመስግኖበታል (የደስታ መግለጫ በመሆኑ አንተ ደስታ የምትሰጥ ሃዘናችንንም የምታርቅ አምላክ ነህ ሲሉ ነው)
🌿- ዘንባባ ደርቆ እንደገና ህይወት ይዘራል የደረቀ ሕይወታችንን የምታለመልም አምላክ ነህ ሲሉ ነው
🌿- ዘንባባ የሰላም ምልክት ነው የሰላም አምልክ ነህ ሲሉ ነው
🌿- ዘንባባ እሾሃማ ነው አንተ ህያው አሸናፊ አምላክ ነህ ሲሉ ነው
🌿- ዘንባባ እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል እንጅ ጌታም አንተ ባህርይህ የማይመረመር ነው ሲሉ ነው
🌿- ዘንባባ የነፃነት ምልክት ነው ከባርነት ነፃ የምታወጣን አንተነህ ሲሉ ነው ይህንኑ አርአያ አድርገን እኛም እንዲሁ እናደርጋለን
"እነሆ ዛሬ እኛ ክርስቲያኖች እግዚአብሔር የሰራትን ቀን ይህች ነችና ሐሴትን እናድርግ " መዝ 117 (118) ÷ 24....ይቆየን
እንደ አህያይቱ እኛም ከእስራታችን ሁሉ ተፈተን የሰላም ባለቤት የሆነውን መዳኃኔ ዓለም ክርስቶስን በልባችን ከተማነት የምናሳድር እውነተኛ ክርስቲያኞች ያደርገን ዘንድ የእርሱ ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን ለዘለዓለሙ አሜን❤️
ሀሳብ ጥቆማ ጥያቄና አስተያየታችሁን @YEAWEDIMERITE ላይ አድርሱን።
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
ት.ዘካ 9÷9
ይህ በነቢዩ ዘካሪያስ አስቀድሞ በትንቢት የተነገረ አማናዊ ቃል የተፈፀመው በኢየሩሳሌም ከተማ ደብረ ዘይት አቅራቢያ ቤተ ፋጌ በምትባል መንደር ነው::ጊዜው በግምት 2000ዓመት ገደማ ይሆናል::ከተማዋ በደስታ ታምሳለች የኢየሩሳሌም ከተማ በተለያዮ ጊዜያት ልዮ ልዮ ነገስታት በሰረገላ ተቀምጠው ጎብኝተዋታልች፣ገስተዋታል የዛሬው ግን ልዮ ንጉሥ ነው ስለ ፍቅር ሲል የእሳት ሰረገላውን ትቶ አህያን የመረጠ አበ ትህትና(የትህትና አባት)መድኃኒት የሆነ ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው::ሕዝቡም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመምጣት ላይ እንዳለ ሲያውቅ ሊቀበለው ወጣ አጠገቡም ሲደርሱ ልብሳቸውን በአህያዪቱ ውርንጭላ ላይ አንጥፈው አስቀመጡት፡፡ አንዳንዶች ያልፍበት በነበረ መንገድ ልብሳቸውን እንዳንዶቹ ደግሞ የዘንባበ ዝንጣፊ ያነጥፉ ነበር፡፡ማቴ 21÷1-17 ከፊትና በኋላ ያሉት ብዙ ሰዎችም “ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ! በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው! ሆሳዕና በአርያም!” እያሉ ይጮኹ ነበር።
ሆሳዕና ማለት መድኃኒት ማለት ነው ሕዝቡም እንዲ ማለታቸው አቤቱ አሁን አድን ብሎ መዝሙረኛው ዳዊት የተናገረውን ንግግር ሲገልጡ ነው ።አህያይቱ ተሰርቃ ከነ ልጆ ከነ(ውርንጭላዋ) ታሰረች ነበር ያሰራት ሰው ሌባ ነወ የሌላ ሰው ንብረት እንደ ንብረቱ አድርጎ ከደጃፉ አስሯታልና ሌባው በቤቱ ያቆያት 5ቀን ተኩል ነው" የማታ የማታ እውነት ይረታ" እንዲሉ አበው እውተኛ ፈራጅ በወጣ ጊዜ አህያዋ ከእስራቷ እንድትፈታ አደረገ ::አህያዋ ና ውርንጫላዋ አዳምና ልጆቹ ሲሆኑ ሌባው ዲያቢሎስ ነው: በአሰት ንግግር እግዚአብሔርን ከመሰለ አምላክ ገነት ከምታክል ቦታ ለይቶ ለ5ቀን ተኩልያክል ጊዜ በሲዖል አስሮናል::
5500 ዘመን ሙሉ በእግረ አጋንንት ተይዘን ሰንጨነቅ መድኃኒት ከሆነው ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ማንም አልደረሰልንም ነበርና ስለዚህ በደስታ ተሞልተው የሆሳዕና አሉ ::
ለምን በአህያና በአህያ ወርንጭላ ላይ ተቀመጠ ቢሉ?
✝እናቲቱ አህያ የብሎይ ውርንጭላይቱ የአዲስ ኪዳን ምሳሌ ናቸው በሁለቱ መቀመጡ ኦሪትን እንዳልሻረ ወንጌልንም እንደሰጠ ሲያጠይቅ አንድም እናቲቱ አህያ ሸክም የለመደች ነች አዲሲቱ ውርንጫይቱ ግን ሽክም ያለመደች የቤተ አሕዛብና የቤተ እስራኤል ምሳሌ ናቸው::ኦሪት ከባድ ወንጌል ግን ቀሊል ናትና አንድም ሕግ የለመዱና ሕግ ያለመዱ እዝቦች ናቸውና:: አንድም አህያ በወለደችሁ ታርፋለች እንዲሉ ኦሪትም በወንጌል ታግዛ ጸንታለችና ነው::ሌላው
👉ፋረስና በቅሎ ለጦርነት ይሁላሉ አህያ ግን አትውልም ጥንት ነቢያት ክፉ ትንቢትና ክፎ ወሬ ይዘው ሲመጡ ማቅ ለብሰው ትቢያ ነስንሰው በፈረስ ወይም በበቅሎ ተቀምጠው ወደ ከተማ ይባሉ መልካም ዜናና ትንቢት ይዘው የመጡ እንደሆነ ደግሞ በአህያ ላይ ተቀምጠው ይመጣሉ ሕዝቡም መቀመጫቸውን አይቶ መልካም ዜና እንዳመጡ ተረድቶ በደስታ ይበቀላቸው ነበርና ጌታችንም መልካም የድኅነት ዜና ሆኜ መጣው ሲል ከቤተ ፋጌ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ በአህያ ላይ ተቀመጠ::
👉በአህያ ተቀምጦ እንደሚመጣ በኦሪት የተነገሩ የኢሳይያስና የዘካሪያስን ትንቢት' ለመፈጸም ነው::(ትንቢቱን ለመፈጸም) ዘካ9÷9
👉ከእኔ ተማሩ እኔ የዋህ በልቤም ትሁት ነኝና እንዳለ ትዕትናን ለማስተማር ማንንም አትናቁ ሲል ማቴ11÷29 ዮሐ13÷1
👉በፈረስና በበቅሎ ያለን ሰው ማንም አይደርስበትም በአህያ ያለን ሰው ግን በቶሎ ይደርሱበታል ስለዚህ እኔ የቅርብ አምላክ ነኝ እንጂ የእሩቅ አምላክ አይደለሁም ከፈለጋችሁን በቅርብ ታገኙኛላችሁ ለማለት በአህያ ተቀመጠ ኤር 23÷23
🌴ሕዝቡ የዘንባባ ዝንጣፊ መያዛቸው🌴
🌿- ይስሐቅ በተወለደ ጊዜ አብርሃም ደስ ብሎት ዘንባባ ይዞ እግዚአብሔርን አመስግኖበታል (የደስታ መግለጫ በመሆኑ አንተ ደስታ የምትሰጥ ሃዘናችንንም የምታርቅ አምላክ ነህ ሲሉ ነው)
🌿- ዘንባባ ደርቆ እንደገና ህይወት ይዘራል የደረቀ ሕይወታችንን የምታለመልም አምላክ ነህ ሲሉ ነው
🌿- ዘንባባ የሰላም ምልክት ነው የሰላም አምልክ ነህ ሲሉ ነው
🌿- ዘንባባ እሾሃማ ነው አንተ ህያው አሸናፊ አምላክ ነህ ሲሉ ነው
🌿- ዘንባባ እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል እንጅ ጌታም አንተ ባህርይህ የማይመረመር ነው ሲሉ ነው
🌿- ዘንባባ የነፃነት ምልክት ነው ከባርነት ነፃ የምታወጣን አንተነህ ሲሉ ነው ይህንኑ አርአያ አድርገን እኛም እንዲሁ እናደርጋለን
"እነሆ ዛሬ እኛ ክርስቲያኖች እግዚአብሔር የሰራትን ቀን ይህች ነችና ሐሴትን እናድርግ " መዝ 117 (118) ÷ 24....ይቆየን
እንደ አህያይቱ እኛም ከእስራታችን ሁሉ ተፈተን የሰላም ባለቤት የሆነውን መዳኃኔ ዓለም ክርስቶስን በልባችን ከተማነት የምናሳድር እውነተኛ ክርስቲያኞች ያደርገን ዘንድ የእርሱ ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን ለዘለዓለሙ አሜን❤️
ሀሳብ ጥቆማ ጥያቄና አስተያየታችሁን @YEAWEDIMERITE ላይ አድርሱን።
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit
👉 @AwediMeherit