#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ብራዚልና ኮሎምቢያ ድንበር/አማዞን ደን ውስጥ
‹‹ካርሎስ››
‹‹አቤት››
‹‹ሀገሬ ኢትዬጵያ አባ..ይን ጨምሮ የብዙ ወንዞች ባለቤት ነች..ማለት የፈለኩት ብዙ ወንዞችን አይቼ አውቃለው…እና አማዞን እጅግ ገራሚ ከሆኑ ጥቂጥ ተፈጥሮዎች መካከል አንዱ ሆኖ ነው ያገኘሁት››
‹‹ምኑ ነው ያስገረመሽ?››
‹‹አማዞን አንዴ ወንዝ ይመስላል….አንዴ ደግሞ ሀይቅ ይሆናል ፣አሁን ተሸገርኩት ብለህ ለሳዕታት ከተጓዝክ በኃላ መልሶ ፊትህ ይጋረጣል››
‹‹ጥሩ ታዝበሻል፡፡አማዞን እና ገባር ወንዞቹ በአጠቃላይ ከ25,000 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው የውስጥ የውሃ መስመሮች መገናኛ ዋና ደም ስር ነው።ይህ ወንዝ ከተለያዩ ሀይቆች ጋር በሚገናኙበት ጊዜ, የወንዙ ጥልቀት 100 ሜትር ይደርሳል፡፡በበጋ ወቅት አማዞን 11 ኪሎ ሜትር ስፋት ሲደርስ 110 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ቦታን ያካልላል፡፡ዝናብ ሲሆን ደግሞ ስፈቱና ጥልቀቱ በሶስት እጥፍ ይጨምራል፡፡ በዚህ ወቅት የወንዙ ውሃ እስከ 20 ሜትር ከፍ ብሎ ስፋቱ ደግሞ 350 ሺህ ካሬ ኪሎ ሜትር መሬት ይሸፍናል፡፡በአማዞን እና ገባር ወንዞቹ ውስጥ ወደ 3,000 የሚጠጉ የዓሣ ዝርያዎች አሉበት››
ስለአማዞን ጥልቅ የሆነ እውቀት እንዳለው አመነች፡፡ ርእሱን ቀይራ‹‹እንስሳቱ ግን አያሳዝኑም››ስትል ጠየቀችው
‹‹እንዴት ማለት?››
‹‹አንድ አንድን ሲበላ …ጠገብኩ እፎይ ብሎ አረፍ ሲል በሌላው ደግሞ ሲበላ…››
‹‹አዎ ሁሉም እንስሳት ሰውንም ጭምር… ሁለችንም ለመብላትም ለመበላትም ነው የተፈጠርነው…፡፡››
‹‹የሰው ልጅ ደግሞ ይበላል እንጂ ይበላል እንዴ?››
‹‹አዎ … ወይ ቀን ሲጥለው ወይ ደግሞ ቀነ ሲጥል ይበላል፡፡አሁን እኔና አንቺ እዚህ ደን ውስጥ ስንት ቀን ከአውሬ መበላት ተርፈናል…ቀን ቢጥለን መበላታችን ይቀር ነበር…ባለፈው ከጓደኞቼ አንዱ በአናኮንዳ ሲበላ አላየሽም?፡፡
‹‹ያ እኮ ተዲያ ከመቶ ሚሊዬን አንድ የሚያጋጥም ነው፡፡››
‹‹አዎ ..ይሄ የሆነው የሰው ልጅ የሚያስብ እንስሳት በመሆኑ እራሱን ከዚህ አደጋ ለመጠበቅ ምን ማድረግ እንዳለበት እያሰበ እያሰበ መጣና እራሱን ከእንስሳ መኖሪያ እያራቀ መንደርና ከተማ እየሰራ ደህንነቱን ለማስጠበቅ ቻለ..እንደዛም ሆኖ ግን እድሜውን ማርዘም ቻለ እንጂ ሄዶ ሆዶ ከመበላት አይተርፍም….አሁን ስንቶቻችን ነን እርስ በርስ እየተባላላን ያለነው…?እኛ አሁን እዚህ ደን ውስጥ መከራችንን እያየን ያለነው ለምንድነው? በመሰል የሰው ልጆች ላለመበላት አይደል፡፡መበላት ሲባል የግድ ሰጋችንን ፈጭተው መዋጥ የለባቸውም …ከገደሉንና ከህይወት መስመር አንሸራተው ካስወጡን በሉን ማለት ነው፡፡››
‹‹ትክክል ነህ፡፡››
‹‹አዎ ትክክል ነኝ፡፡ ግን ደግሞ ሁሉም እንስሳት እኩል የመብላትና መበላት እጣ አላቸው ማለት አይደለም፡፡የጫካው ህግ የምግብ ስርዓት ልክ እንደፒራሚድ ነው፡፡ከፒራሚዱ የስረኛው ወለል ያሉ መበላት የየእለት ጭንቀታቸውና እጣቸው ነው፡፡የፒራሚዲ ጫፍ ያሉት ደግሞ እነአንበሳ ነብር የመሳሰሉትና ማለቴ ነው..ማደን መያዝና መዘንጠል የየእለት ስራቸውና ተግባራቸው ነው፡፡››
‹‹ተመስገን እኛ የሰው ልጅ እንደዚህ አለመሆናችን፡፡››
ፈገግ ብሎ ሳቀባት፡፡
‹‹ምነው ትክክል አይደለሁም እንዴ?››
አይ እንደውም ይሄንን ፒራሚዱን የምግብ ስርዓት ከእንስሳቱ ኮርጆ የራሱን ማሻሻያ አድርጎበት በጥበብ ነው እየተገበረ ያለው፡፡የአለም 90 ፐርሰንት ሀብት በ10 ፐርሰንት በሚሆኑ ቱጃሮች እጅ ነው ያለው ..ያ ማለት በሰው ልጅ ኪንግደም ውስጥ 10 ፐርሰንቱ የፒራሚዱ ጫፍ ላይ ያሉት ናቸው፡፡እነሱ የ90 ፐርሰንቱን ላብና ወዝ በተለያ ሚስጥራዊና ዘዴ ቅርጥፍ አድርጎ ይሰለቅጡታል፡፡››
አይን አይኗን በስስት እያያት‹‹ስለአንቺ ሳስብ ምን እንደሚገርመኝ ታውቂያለሽ?››አላት
የተወሰነ ጉጉት በሚታይበት የስሜት መነቃቃት‹‹እስኪ ምንድነው ንገረኝ ልስማው ››ስትል መለሰችት
‹‹ያንቺ ነፍስ ያንቺ ብቻ እንዳልሆነች ነው እንድረዳ ያደረግሺኝ..የነፍስሽ ክፍያ የወንድምሽ ንበረት ነው የሚመስለው፡፡አደራ አንቺ ጋር አስቀምጪልኝ ብሎ እንደሰጠሸና ያንን አደራሻን ላለመብላት የመጨረሻውን ጥረት እየጣርሽ እንደሆነ ነው፡፡ያ ነው እንዲህ ብርቱና ጠንካራ እንድትሆኚ ያደረገሽ….››
‹‹ጥሩ ገልፀሀዋል..ግን ይሄ የእኔ ብቻ ችግር አይመስለኝም፡፡የሰው ልጅ ሁሉ ለቤተሰቡ ይብዛም ይነስ እንጂ ተመሳሳይ አይነት እይታ አለው፡፡ማንም ቢሆን ነፍሱ የእሱ ብቻ አይደለም…እሱ ሲያመው የሚያማቸው እሱ ሲደሰት ደስ የሚላቸው ቤተሰቦች ይኖሩታል፡፡ለእነሱ ሲል እራሱን ከአደጋ ይጠብቃል..ለእነሱ ሲል ጠንክሮ ይሰራል፡፡አዎ ጠንካራ የቤተሰብ ትስስር ያለው ሰው ጠንካራ ስብዕና ይኖረዋል፡፡እነሱ በህይወት ጉዞ ትክክለኛውን መስመር መርቶ እንዲጓዝ ብርታትና ጥንካሬ ይሆኑታል፡፡.አብዛኛው ሰው የሚኖርላቸው የሚወዳቸውና የሚወዱት አምስት ወይም አስር ሰዎች ይሩታል፡፡እኔ የእኔ የምለው አንድ ወንድሜ ብቻ ስለሆነ ነው፡፡ያለኝን ፍቅር ጠቅላላ ተሰብስቦና ተከማችቶ አንድ ወንድሜ ላይ ስላረፈ ነው፡፡››
‹‹ገባኝ ..ጥሩ ገልፀሸዋል….ቀናሁበት››
‹‹ግድ የለህም አትቅና፡፡ ፍቅር ከመጠን ሲያልፍ ትንፋሽ ይነሳል…እንዲህ እንደምታስበው ጥሩ ጎን ብቻ አይደለም ያለው፡፡ወንድሜ የ10 ደቂቃ ታላቄ ወይም በሌላ አገላለፅ መንትያዬ ነው፡፡አንድ ማህፀን ውስጥ አንድ አይነት ሰዓት አንድ አይነት ምግብ እየተመገብን ነው የኖርነው…ከተወለድንም በኃላ እንደዛው… ቢሆንም በተለይ ወላጆቻችን ከሞቱ በኃላ ልክ እንደታናሽ ወንድሜ ነው የምቆጣጠረው፡፡የት ገባህ?የት ወጣህ….?በዚህ ግባ በዚህ ውጣ..አንዳንዴ ጭቅጭቄ ለእኔ ለራሴ ይሰለቸኛል..የሚገርመኝ እሱ ግን የእኔን ጭቅጭቅ የሚታገስበት የሚገርም ትእግስት አለው….ዝም ያልኩት ቀን እንደውም ምን ነካት ብሎ ይንቆራጠጣል….፡፡››
…
አዲስአበባ
///
ናኦል ከምስራቅ ጋር እንደተቃጠሩት በማግስቱ ምሽት 1፡30 ነበር ቦሌ የደረሰው፡፡
‹‹ለሁለት 10 ጉዳይ ሲል ልደውልላት ወይስ ሁለት ሰዓት ይሙላ?›› እያለ ከራሱ ጋር ሲሞገት ከፊት ለፊት ሽክ ያለ አለባበስ ለብሳ በአስፈሪ ግርማ ሞገሶ አንድ መለስተኛ ዘመናዊ ሻንጣ በእጇ በመጎተት እያሽከረከረች ወደእሱ ስትቀርብ ተመለከተ፡፡ፊቱ ሁሉ አንፀባረቀ፡፡
‹‹እሺ..ቀድመህ ነው የደረስከው››አለችው፡፡
‹‹አዎ መቅደምም ነበረብኝ…ግን ሻንጣው ለምን አስፈለገ …?የሚያስፈልጉኝን ነገሮች እንደማልይዝ ጠርጥረሽ ነው አይደል? ዝም ብለሽ ነው የሰጋሽው፡፡››አለ፡፡እሱ ..ሻንጣውን ለእሱ ብላ የሚያስፈልጉትን እቃዎች ይዛበት የመጣች ነው የመሰለው፡፡
‹‹አይ ጎረምሳው ተሳስተሀል..ይሄ ሻንጣ የእኔ ነው፡፡››
‹‹የእኔ ነው ማለት?››
‹‹የእኔ ነዋ …እኔም ተጓዥ ነኝ፡፡ይልቅ ና እንግባ፡፡›› አለችና ከፊቱ ቀደመች፡፡
‹‹ወደየት ልትሄጂ ነው.?በአንድ ቀን ሁለታችንም ከአገር እንደምንወጣ አላወቅም ነበር፡፡››
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ብራዚልና ኮሎምቢያ ድንበር/አማዞን ደን ውስጥ
‹‹ካርሎስ››
‹‹አቤት››
‹‹ሀገሬ ኢትዬጵያ አባ..ይን ጨምሮ የብዙ ወንዞች ባለቤት ነች..ማለት የፈለኩት ብዙ ወንዞችን አይቼ አውቃለው…እና አማዞን እጅግ ገራሚ ከሆኑ ጥቂጥ ተፈጥሮዎች መካከል አንዱ ሆኖ ነው ያገኘሁት››
‹‹ምኑ ነው ያስገረመሽ?››
‹‹አማዞን አንዴ ወንዝ ይመስላል….አንዴ ደግሞ ሀይቅ ይሆናል ፣አሁን ተሸገርኩት ብለህ ለሳዕታት ከተጓዝክ በኃላ መልሶ ፊትህ ይጋረጣል››
‹‹ጥሩ ታዝበሻል፡፡አማዞን እና ገባር ወንዞቹ በአጠቃላይ ከ25,000 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው የውስጥ የውሃ መስመሮች መገናኛ ዋና ደም ስር ነው።ይህ ወንዝ ከተለያዩ ሀይቆች ጋር በሚገናኙበት ጊዜ, የወንዙ ጥልቀት 100 ሜትር ይደርሳል፡፡በበጋ ወቅት አማዞን 11 ኪሎ ሜትር ስፋት ሲደርስ 110 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ቦታን ያካልላል፡፡ዝናብ ሲሆን ደግሞ ስፈቱና ጥልቀቱ በሶስት እጥፍ ይጨምራል፡፡ በዚህ ወቅት የወንዙ ውሃ እስከ 20 ሜትር ከፍ ብሎ ስፋቱ ደግሞ 350 ሺህ ካሬ ኪሎ ሜትር መሬት ይሸፍናል፡፡በአማዞን እና ገባር ወንዞቹ ውስጥ ወደ 3,000 የሚጠጉ የዓሣ ዝርያዎች አሉበት››
ስለአማዞን ጥልቅ የሆነ እውቀት እንዳለው አመነች፡፡ ርእሱን ቀይራ‹‹እንስሳቱ ግን አያሳዝኑም››ስትል ጠየቀችው
‹‹እንዴት ማለት?››
‹‹አንድ አንድን ሲበላ …ጠገብኩ እፎይ ብሎ አረፍ ሲል በሌላው ደግሞ ሲበላ…››
‹‹አዎ ሁሉም እንስሳት ሰውንም ጭምር… ሁለችንም ለመብላትም ለመበላትም ነው የተፈጠርነው…፡፡››
‹‹የሰው ልጅ ደግሞ ይበላል እንጂ ይበላል እንዴ?››
‹‹አዎ … ወይ ቀን ሲጥለው ወይ ደግሞ ቀነ ሲጥል ይበላል፡፡አሁን እኔና አንቺ እዚህ ደን ውስጥ ስንት ቀን ከአውሬ መበላት ተርፈናል…ቀን ቢጥለን መበላታችን ይቀር ነበር…ባለፈው ከጓደኞቼ አንዱ በአናኮንዳ ሲበላ አላየሽም?፡፡
‹‹ያ እኮ ተዲያ ከመቶ ሚሊዬን አንድ የሚያጋጥም ነው፡፡››
‹‹አዎ ..ይሄ የሆነው የሰው ልጅ የሚያስብ እንስሳት በመሆኑ እራሱን ከዚህ አደጋ ለመጠበቅ ምን ማድረግ እንዳለበት እያሰበ እያሰበ መጣና እራሱን ከእንስሳ መኖሪያ እያራቀ መንደርና ከተማ እየሰራ ደህንነቱን ለማስጠበቅ ቻለ..እንደዛም ሆኖ ግን እድሜውን ማርዘም ቻለ እንጂ ሄዶ ሆዶ ከመበላት አይተርፍም….አሁን ስንቶቻችን ነን እርስ በርስ እየተባላላን ያለነው…?እኛ አሁን እዚህ ደን ውስጥ መከራችንን እያየን ያለነው ለምንድነው? በመሰል የሰው ልጆች ላለመበላት አይደል፡፡መበላት ሲባል የግድ ሰጋችንን ፈጭተው መዋጥ የለባቸውም …ከገደሉንና ከህይወት መስመር አንሸራተው ካስወጡን በሉን ማለት ነው፡፡››
‹‹ትክክል ነህ፡፡››
‹‹አዎ ትክክል ነኝ፡፡ ግን ደግሞ ሁሉም እንስሳት እኩል የመብላትና መበላት እጣ አላቸው ማለት አይደለም፡፡የጫካው ህግ የምግብ ስርዓት ልክ እንደፒራሚድ ነው፡፡ከፒራሚዱ የስረኛው ወለል ያሉ መበላት የየእለት ጭንቀታቸውና እጣቸው ነው፡፡የፒራሚዲ ጫፍ ያሉት ደግሞ እነአንበሳ ነብር የመሳሰሉትና ማለቴ ነው..ማደን መያዝና መዘንጠል የየእለት ስራቸውና ተግባራቸው ነው፡፡››
‹‹ተመስገን እኛ የሰው ልጅ እንደዚህ አለመሆናችን፡፡››
ፈገግ ብሎ ሳቀባት፡፡
‹‹ምነው ትክክል አይደለሁም እንዴ?››
አይ እንደውም ይሄንን ፒራሚዱን የምግብ ስርዓት ከእንስሳቱ ኮርጆ የራሱን ማሻሻያ አድርጎበት በጥበብ ነው እየተገበረ ያለው፡፡የአለም 90 ፐርሰንት ሀብት በ10 ፐርሰንት በሚሆኑ ቱጃሮች እጅ ነው ያለው ..ያ ማለት በሰው ልጅ ኪንግደም ውስጥ 10 ፐርሰንቱ የፒራሚዱ ጫፍ ላይ ያሉት ናቸው፡፡እነሱ የ90 ፐርሰንቱን ላብና ወዝ በተለያ ሚስጥራዊና ዘዴ ቅርጥፍ አድርጎ ይሰለቅጡታል፡፡››
አይን አይኗን በስስት እያያት‹‹ስለአንቺ ሳስብ ምን እንደሚገርመኝ ታውቂያለሽ?››አላት
የተወሰነ ጉጉት በሚታይበት የስሜት መነቃቃት‹‹እስኪ ምንድነው ንገረኝ ልስማው ››ስትል መለሰችት
‹‹ያንቺ ነፍስ ያንቺ ብቻ እንዳልሆነች ነው እንድረዳ ያደረግሺኝ..የነፍስሽ ክፍያ የወንድምሽ ንበረት ነው የሚመስለው፡፡አደራ አንቺ ጋር አስቀምጪልኝ ብሎ እንደሰጠሸና ያንን አደራሻን ላለመብላት የመጨረሻውን ጥረት እየጣርሽ እንደሆነ ነው፡፡ያ ነው እንዲህ ብርቱና ጠንካራ እንድትሆኚ ያደረገሽ….››
‹‹ጥሩ ገልፀሀዋል..ግን ይሄ የእኔ ብቻ ችግር አይመስለኝም፡፡የሰው ልጅ ሁሉ ለቤተሰቡ ይብዛም ይነስ እንጂ ተመሳሳይ አይነት እይታ አለው፡፡ማንም ቢሆን ነፍሱ የእሱ ብቻ አይደለም…እሱ ሲያመው የሚያማቸው እሱ ሲደሰት ደስ የሚላቸው ቤተሰቦች ይኖሩታል፡፡ለእነሱ ሲል እራሱን ከአደጋ ይጠብቃል..ለእነሱ ሲል ጠንክሮ ይሰራል፡፡አዎ ጠንካራ የቤተሰብ ትስስር ያለው ሰው ጠንካራ ስብዕና ይኖረዋል፡፡እነሱ በህይወት ጉዞ ትክክለኛውን መስመር መርቶ እንዲጓዝ ብርታትና ጥንካሬ ይሆኑታል፡፡.አብዛኛው ሰው የሚኖርላቸው የሚወዳቸውና የሚወዱት አምስት ወይም አስር ሰዎች ይሩታል፡፡እኔ የእኔ የምለው አንድ ወንድሜ ብቻ ስለሆነ ነው፡፡ያለኝን ፍቅር ጠቅላላ ተሰብስቦና ተከማችቶ አንድ ወንድሜ ላይ ስላረፈ ነው፡፡››
‹‹ገባኝ ..ጥሩ ገልፀሸዋል….ቀናሁበት››
‹‹ግድ የለህም አትቅና፡፡ ፍቅር ከመጠን ሲያልፍ ትንፋሽ ይነሳል…እንዲህ እንደምታስበው ጥሩ ጎን ብቻ አይደለም ያለው፡፡ወንድሜ የ10 ደቂቃ ታላቄ ወይም በሌላ አገላለፅ መንትያዬ ነው፡፡አንድ ማህፀን ውስጥ አንድ አይነት ሰዓት አንድ አይነት ምግብ እየተመገብን ነው የኖርነው…ከተወለድንም በኃላ እንደዛው… ቢሆንም በተለይ ወላጆቻችን ከሞቱ በኃላ ልክ እንደታናሽ ወንድሜ ነው የምቆጣጠረው፡፡የት ገባህ?የት ወጣህ….?በዚህ ግባ በዚህ ውጣ..አንዳንዴ ጭቅጭቄ ለእኔ ለራሴ ይሰለቸኛል..የሚገርመኝ እሱ ግን የእኔን ጭቅጭቅ የሚታገስበት የሚገርም ትእግስት አለው….ዝም ያልኩት ቀን እንደውም ምን ነካት ብሎ ይንቆራጠጣል….፡፡››
…
አዲስአበባ
///
ናኦል ከምስራቅ ጋር እንደተቃጠሩት በማግስቱ ምሽት 1፡30 ነበር ቦሌ የደረሰው፡፡
‹‹ለሁለት 10 ጉዳይ ሲል ልደውልላት ወይስ ሁለት ሰዓት ይሙላ?›› እያለ ከራሱ ጋር ሲሞገት ከፊት ለፊት ሽክ ያለ አለባበስ ለብሳ በአስፈሪ ግርማ ሞገሶ አንድ መለስተኛ ዘመናዊ ሻንጣ በእጇ በመጎተት እያሽከረከረች ወደእሱ ስትቀርብ ተመለከተ፡፡ፊቱ ሁሉ አንፀባረቀ፡፡
‹‹እሺ..ቀድመህ ነው የደረስከው››አለችው፡፡
‹‹አዎ መቅደምም ነበረብኝ…ግን ሻንጣው ለምን አስፈለገ …?የሚያስፈልጉኝን ነገሮች እንደማልይዝ ጠርጥረሽ ነው አይደል? ዝም ብለሽ ነው የሰጋሽው፡፡››አለ፡፡እሱ ..ሻንጣውን ለእሱ ብላ የሚያስፈልጉትን እቃዎች ይዛበት የመጣች ነው የመሰለው፡፡
‹‹አይ ጎረምሳው ተሳስተሀል..ይሄ ሻንጣ የእኔ ነው፡፡››
‹‹የእኔ ነው ማለት?››
‹‹የእኔ ነዋ …እኔም ተጓዥ ነኝ፡፡ይልቅ ና እንግባ፡፡›› አለችና ከፊቱ ቀደመች፡፡
‹‹ወደየት ልትሄጂ ነው.?በአንድ ቀን ሁለታችንም ከአገር እንደምንወጣ አላወቅም ነበር፡፡››
👍59❤5👏2🔥1🥰1