#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...“ቤተመንግሥት ገብተሻል አሁን ዐዲስ ወግ አምጫ እንግዲህ
አሏት፣ ምጸት በተቀላቀለው አነጋገር። ቀጠሉና፣ “አንቺ ብትሆኚ ኑሮ ምን ታረጊ ኑሯል? እስቲ በይ ንገሪኝ” አሏት።
“እኔማ እዚያ ማን አድርሶኝ ... ብቻ መላ ፈልግ ነበር።”
“መላ? ለነገሩ አንቺ መለኛ ነሽ።”
ፈገግ ብላ ዝም አለች።
“ምን አይተሽ የኔ እህት” ሲሉ ቀጠሉ። “አንዳንዶቹ ሲነግሡ
ሲሻቸው የገዛ ወንድሞቻቸውን እጅና እግር እየቆረጡ ነው እወህኒ
ሚሰዱ... እንዳይነግሡ” አሉና አፄ በካፋ ወንድማቸውን አቤቶ ዮሐንስን አንድ እጃቸውን ማስቆረጣቸውን ሊነግሯት ፈለጉና ለራሳቸው ወደ ፊት ትደርስበት የለ? ብለው ለእሷ፣ “ኣካሉ የጎደለ ደሞ መንገሥ አይችል” አሏት።
“ስለምን? አካሉ ቢጎልስ?”
“አካሉ ኸጎደለ እንዴት ብሎ ጦር ይመራል? እስቲ ንገሪኝ በይ?
ብቻ አሁን እሱን ተይውና ስንት የሞቱ ነገሥታት ዝርያዎች አሉ
መሰለሽ ኸተራራው... እወህኒ አምባ። ወህኒ አምባ ማለት ለጐንደር ቅርብ ናት... ኸማክሰኚት ብዙም አትርቅ። ብቻዋን የቆመች ተራራ ናት። አንድ በር ብቻ ነው ያላት። አናቷ ሜዳ፣ መውጫም መውረጃም የላት። ኸዛው ኻምባው ላይ የደንጊያ ቤቶችም አሉ።”
ወለተጊዮርጊስ የሰማችው ሁሉ እንግዳ ነገር ሆነባት። “ዛዲያ እንዴት ነው ሰዎቹ ከተራራው ሚወጡ ሚወርዱ?”
“በመጫኛ። ተራራይቱን ኻየሻት ዝንዥሮ ወይ ጦጣ መሆን ኣለብሽ
እዛ ላይ ለመውጣትም ሆነ ለመውረድ። ዙርያዋ ጥድ ነው። ምሽግም አላት አሉ። ብቻ እንዳው ንጉሥ ሞተ ኸተባለ ወይ ደሞ አንዱን እናንግሥ ያሉ እንደሁ፣ በቃ እግር ብረቱን ፈታተው ያኮበልሉታል።”
“ጠባቂም የለባቸው?”
“አሉዋቸው እንጂ! ያውም ንጉሡ ራሳቸው የመረጧቸው ወታደሮች
ናቸዋ ሚጠብቁ! ወታደሮቹ ዘብ ሚቆሙበት ቦታ ሁሉ አለ እኮ።
ወታደሮቹ ኸቀደሙ ነገሥታት ልገባች እንዳይመሳጠሩ፣ ለንጉሡ
መሐላ ገብተው ነው ሚጠብቁ። ኸዛ ቦታ ያለ ንጉሡ ፈቃድ ማንም
ሊገባ ወይም ሊወጣ አይችልም። ግና ለዘበኞቹ ጉርሻ ይሰጧቸዋል።
ለጉርሻ ማይተኛ ስንት አለ? የሰው ልዥ እኮ ተላላ ነው፣ በቀላሉ
ይደለላል። ዛዲያ ለእንዲህ ያለው ክደት ቅጣቱ ሞት ነው። እንንገሥ
ባዮቹም አንዴ ኸተራራይቱ ኸወረዱ፣ ጭፍራ አስከትለው ጫካ ይገባሉ፣ ኸዚያ ነፍጥ ይዘው ገስግሰው ይመጣሉ። እልቂት ነው አልሁሽ ኸዝያ ወዲያ። አንዴ ያችን አልጋ ኸመዳፋቸው ኻረጉ ወዲያ ደሞ ሹም ሽር ያረጋሉ። ኸባላገሩ ርስት እህላሙን መሬት እየመረጡ ለሚፈልጉት በጉልት ይሰጣሉ፣ ሲፈልጉ ርስት ይተክላሉ፣ ገባርም ይሰጣሉ፣ ከብትም እንዲወስዱ ያረጋሉ። የጃንሆይ አባት አጤ አድያም ሰገድ ኢያሱ ሰላም አምጥተው እሳቸው ከሞቱ በኋላ፣ ረብሻ፣ ጦር ሰበቃ ሆነ።
የጭንቅ ዘመን ነበር።”
ዮልያና፣ ስመ መንግሥታቸው አድያም ሰገድ የሆነው ቀዳማዊ ኢያሱ ከሞቱ በኋላ፣ የነገሡ ነገሥታት ተክለሃይማኖት፣ ቴዎፍሎስ፣ ዮስጦስና ሣልሳዊ ዳዊት፣ እያንዳንዳቸው ለአጭር ጊዜ እየገዙ ሃገሪቱ ሰላም
አጥታ ስትታመስ፣ በሃይማኖት ክርክርና ንትርክ ስትብረከረክ ብሎም በእልቂት ስትንጠራወዝ እንደነበረች በዝርዝር ሊነግሯት ፈልገው፣ ፊቷ ላይ በግልፅ የሚታየውን የመሸበር ስሜት አስተውለው ዝም አሉ።
ወለተጊዮርጊስ የሰማችው ነገር ሁሉ ከበዳት። ቤተመንግሥት
መግባት አስፈሪ ነገር ሆነባት። ፋሲል ቤተመንግሥት ቅጥር ግቢ
ስትገባ ያየችው ግርማ ሞገስ ሁሉ በውስጡ የማይመጥኑት አናሣ
ነገሮች ያቀፈ መሰላት።
“ማትቀመጪ? ቁመሽ ትዘልቂዋለሽ?” አሏት።
“እሚታዬ ለመሆኑ ሰዎቹ ምን እየበሉ ይኖራሉ፣ኸተራራ
ተቀምጠው?”
“ንጉሡ እኮ ቀለብ ይሰጣል። ውሃም ቢሆን ኸታች ምንጭ አለ::
እነሱም ኸዛው ይዋለዳሉ። ትምርት ይማራሉ፤ ቤተክሲያንም..
ጊዮርጊስና ማርያምም እኮ አሉ ኸዛው።”
“ሚገርም ነው። ስለዝኸ ስታወሪ ሰምቸሽም አላውቅ።”
ትናንት ፋሲለደስ ቤተመንግሥት ግቢ ስትገባ የነበራት የመደነቅ
ስሜት ኹሉ ጠፍቶባት ጭንቀት ያዛት። ለራሷ እኼ ቤተመንግሥት
ሚባል ነገር አስፈሪ ነው አለችና ወደ አልጋው ጫፍ አመራች።
ልብሶቹን በጥንቃቄ ወደ ኋላ ገፋ አድርጋ ተቀመጠች።
“ጌጦቹን አልጋው ላይ አኑሪያቸው” ብለው በቀኝ እጃቸው ኣልጋውን መታ አደረጉት።
“ልብሶቹን ደሞ እመንጠቆዎቹ ላይ ስቀያቸው” አሏት፣ ግድግዳ ላይ የተተከሉትን ከቀንድ የተሰሩ የልብስ መስቀያዎች
በእጃቸው እየጠቆሟት።
ጌጦቹን አልጋው ላይ ትታ ሄዳ ልብሶቹን አንድ በአንድ
ሰቀለቻቸውና ጫማዎቹን መሬት ላይ አስቀምጣ ተመልሳ አልጋው
ጫፍ ላይ ተቀመጠች።
“ምን እያልሽኝ ነበር? አዎ 'ስለዝህ ስታወሪ ሰምቸሽም አላውቅ
ነው ያልሽኝ” አለና፣ “ፊት ብታቂ ኑሮ ምን ይጠቅምሽ ኑሯል?
የዠመርሁትን ልጨርስልሽ እንጂ። ጃንሆይ እንዳልሁሽ በንጉሥ
ዮስጦስ ግዝየ ኸወህኒ አምባ ሲያመልጡ እኝሁ ዮስጦስ መልሰው አሰሯቸው። ያለቤታቸው ገብተው።”
“ያለቤታቸው ገብተው?”
“ዮስጦስ ማለት ልደታ ማርያምን እዝሁ እጐንደር የተከሉት
ያጤ ቴዎፍሎስ እንደራሴ ነበሩ እንጂ የነጋሢ ዘር የላቸውም። ኋላ
ጃንሆይ ደሞ ሲነግሡ ወህኒ አምባ ያሉ የነጋሢ ዝርያዎች ሁሉ የገዛ ወንድሞቻቸው ሳይቀሩ ተንጫጩ።”
“ምን ይሁን ብለው?”
“ሚነግሠውን እኛ እንመርጣለን፤ በካፋ ኃይለኛና ጨካኝ ነው
ብለው። ያው አልቀረም መሲሕ ሰገድ ተብለው ነገሡ። ይነግሣሉ ሚል ንግርትም ነበር። ጃንሆይ ወህኒ ሳሉ በሳቸው ልክ ጧሚና ጠሎተኛ አልነበረም ነው ሚሉ።
ምጥዋትም መስደድ ያዘወትሩ፣ መጻሕፍቱንም ያገላብጡ ነበር። ቅኔ አዋቂም ናቸው። ኸዛው እናታቸው አገር... ዲማ ነው ቅኔውን የተማሩ። ደሞ ምን የመሰለ ታንኳም አሠርተዋል እኮ።
ግብጦች ናቸው አሉ የሠሩላቸው። ኸጣና ነው ያለ...”
ድንገት ደንገጡሮቹ ሲገቡ ዝም አሉ። ሴቶቹ ወለተጊዮርጊስን
አልብሰው፣ አስጊጠውና እላይዋ ላይ ሽቱ አርከፍክፈው ግብር መታደሚያ ሰዐት ሲደርስ እንደሚመለሱና ግብር እንደ ንጉሠ ነገሥቱ ፍላጎትና
እንደ ሁኔታው የተለያየ አዳራሽ ውስጥ እንደሚደረግና ለዛሬ ግን ባለ ሁለት ደርቡ ወርቅ ሰቀላ ምድር ቤት አዳራሽ ውስጥ እንደሚሆን ነግረዋቸው ወጡ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
“ምንትዋብ ብያታለሁ።”
ወርቅ ሰቀላ ጥቁር እንግዳ ለመቀበል ዝግጁ ሆኗል። የእልፍኝ
አስከልካዩ በሥሩ ያሉትን እንደየደረጃቸው ነጠላ ያደገደጉትን፣ ወይም ካባ የደረቡትን ዐራቱን ጭፍሮቹን አሰማርቷል። ጠርዙ ባለወርቅ ቅብ
የሆነው የንጉሠ ነገሥቱ መንበረ መንግሥት የለበሰው የፋርስ ባለቀይ፣ባለሰማያዊና ባለነጭ ምንጣፍ በትክክል መነጠፉን፣ ከጎኑ ያለው ጠርዙ የወርቅ ቅብ የሆነው ድንክ አልጋ ዝግጁ መሆኑንና ከአልጋዎቹ ሥር
የተነጠፈው ቀይ የፋርስ ስጋጃ ላይ የሐር ምንጣፍ በትክክል መነጠፉን አረጋግጧል።
ከንጉሡ መንበር በስተጀርባ ያለውን ግድግዳ በቀይና በልዩ ልዩ
ቀለማት ያጌጠ ከቱርክ የመጣ ምንጣፍ ሸፍኖታል። ድንክ አልጋዎቹ የተቀመጡበትን አካባቢ ከሐር የተሠራ ነጭ አጎበር ከላይ ከልሎታል።አናቱ ላይ የዘውድ ቅርጽ ያለው ጉልላት ተቀምጦለታል። ንጉሠ
ነገሥቱ ሆኑ አብረዋቸው የሚቀመጡት እንግዶች እስኪገቡ አጎበሩ በግራና በቀኝ ያሉ እንጨቶች ላይ በቀጭን ሐር ሻሽ ታስሯል።ሲያስፈልግ የሚጋርዱትና የሚገልጡት ሁለት የቤተመንግሥት ባለሟሎች አደግድገው ግራና ቀኙን ቆመዋል። በአዳራሹ ግራና ቀኝ
ያሉ መስኮቶች የሐር መጋረጃ ተጋርደውባቸዋል።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...“ቤተመንግሥት ገብተሻል አሁን ዐዲስ ወግ አምጫ እንግዲህ
አሏት፣ ምጸት በተቀላቀለው አነጋገር። ቀጠሉና፣ “አንቺ ብትሆኚ ኑሮ ምን ታረጊ ኑሯል? እስቲ በይ ንገሪኝ” አሏት።
“እኔማ እዚያ ማን አድርሶኝ ... ብቻ መላ ፈልግ ነበር።”
“መላ? ለነገሩ አንቺ መለኛ ነሽ።”
ፈገግ ብላ ዝም አለች።
“ምን አይተሽ የኔ እህት” ሲሉ ቀጠሉ። “አንዳንዶቹ ሲነግሡ
ሲሻቸው የገዛ ወንድሞቻቸውን እጅና እግር እየቆረጡ ነው እወህኒ
ሚሰዱ... እንዳይነግሡ” አሉና አፄ በካፋ ወንድማቸውን አቤቶ ዮሐንስን አንድ እጃቸውን ማስቆረጣቸውን ሊነግሯት ፈለጉና ለራሳቸው ወደ ፊት ትደርስበት የለ? ብለው ለእሷ፣ “ኣካሉ የጎደለ ደሞ መንገሥ አይችል” አሏት።
“ስለምን? አካሉ ቢጎልስ?”
“አካሉ ኸጎደለ እንዴት ብሎ ጦር ይመራል? እስቲ ንገሪኝ በይ?
ብቻ አሁን እሱን ተይውና ስንት የሞቱ ነገሥታት ዝርያዎች አሉ
መሰለሽ ኸተራራው... እወህኒ አምባ። ወህኒ አምባ ማለት ለጐንደር ቅርብ ናት... ኸማክሰኚት ብዙም አትርቅ። ብቻዋን የቆመች ተራራ ናት። አንድ በር ብቻ ነው ያላት። አናቷ ሜዳ፣ መውጫም መውረጃም የላት። ኸዛው ኻምባው ላይ የደንጊያ ቤቶችም አሉ።”
ወለተጊዮርጊስ የሰማችው ሁሉ እንግዳ ነገር ሆነባት። “ዛዲያ እንዴት ነው ሰዎቹ ከተራራው ሚወጡ ሚወርዱ?”
“በመጫኛ። ተራራይቱን ኻየሻት ዝንዥሮ ወይ ጦጣ መሆን ኣለብሽ
እዛ ላይ ለመውጣትም ሆነ ለመውረድ። ዙርያዋ ጥድ ነው። ምሽግም አላት አሉ። ብቻ እንዳው ንጉሥ ሞተ ኸተባለ ወይ ደሞ አንዱን እናንግሥ ያሉ እንደሁ፣ በቃ እግር ብረቱን ፈታተው ያኮበልሉታል።”
“ጠባቂም የለባቸው?”
“አሉዋቸው እንጂ! ያውም ንጉሡ ራሳቸው የመረጧቸው ወታደሮች
ናቸዋ ሚጠብቁ! ወታደሮቹ ዘብ ሚቆሙበት ቦታ ሁሉ አለ እኮ።
ወታደሮቹ ኸቀደሙ ነገሥታት ልገባች እንዳይመሳጠሩ፣ ለንጉሡ
መሐላ ገብተው ነው ሚጠብቁ። ኸዛ ቦታ ያለ ንጉሡ ፈቃድ ማንም
ሊገባ ወይም ሊወጣ አይችልም። ግና ለዘበኞቹ ጉርሻ ይሰጧቸዋል።
ለጉርሻ ማይተኛ ስንት አለ? የሰው ልዥ እኮ ተላላ ነው፣ በቀላሉ
ይደለላል። ዛዲያ ለእንዲህ ያለው ክደት ቅጣቱ ሞት ነው። እንንገሥ
ባዮቹም አንዴ ኸተራራይቱ ኸወረዱ፣ ጭፍራ አስከትለው ጫካ ይገባሉ፣ ኸዚያ ነፍጥ ይዘው ገስግሰው ይመጣሉ። እልቂት ነው አልሁሽ ኸዝያ ወዲያ። አንዴ ያችን አልጋ ኸመዳፋቸው ኻረጉ ወዲያ ደሞ ሹም ሽር ያረጋሉ። ኸባላገሩ ርስት እህላሙን መሬት እየመረጡ ለሚፈልጉት በጉልት ይሰጣሉ፣ ሲፈልጉ ርስት ይተክላሉ፣ ገባርም ይሰጣሉ፣ ከብትም እንዲወስዱ ያረጋሉ። የጃንሆይ አባት አጤ አድያም ሰገድ ኢያሱ ሰላም አምጥተው እሳቸው ከሞቱ በኋላ፣ ረብሻ፣ ጦር ሰበቃ ሆነ።
የጭንቅ ዘመን ነበር።”
ዮልያና፣ ስመ መንግሥታቸው አድያም ሰገድ የሆነው ቀዳማዊ ኢያሱ ከሞቱ በኋላ፣ የነገሡ ነገሥታት ተክለሃይማኖት፣ ቴዎፍሎስ፣ ዮስጦስና ሣልሳዊ ዳዊት፣ እያንዳንዳቸው ለአጭር ጊዜ እየገዙ ሃገሪቱ ሰላም
አጥታ ስትታመስ፣ በሃይማኖት ክርክርና ንትርክ ስትብረከረክ ብሎም በእልቂት ስትንጠራወዝ እንደነበረች በዝርዝር ሊነግሯት ፈልገው፣ ፊቷ ላይ በግልፅ የሚታየውን የመሸበር ስሜት አስተውለው ዝም አሉ።
ወለተጊዮርጊስ የሰማችው ነገር ሁሉ ከበዳት። ቤተመንግሥት
መግባት አስፈሪ ነገር ሆነባት። ፋሲል ቤተመንግሥት ቅጥር ግቢ
ስትገባ ያየችው ግርማ ሞገስ ሁሉ በውስጡ የማይመጥኑት አናሣ
ነገሮች ያቀፈ መሰላት።
“ማትቀመጪ? ቁመሽ ትዘልቂዋለሽ?” አሏት።
“እሚታዬ ለመሆኑ ሰዎቹ ምን እየበሉ ይኖራሉ፣ኸተራራ
ተቀምጠው?”
“ንጉሡ እኮ ቀለብ ይሰጣል። ውሃም ቢሆን ኸታች ምንጭ አለ::
እነሱም ኸዛው ይዋለዳሉ። ትምርት ይማራሉ፤ ቤተክሲያንም..
ጊዮርጊስና ማርያምም እኮ አሉ ኸዛው።”
“ሚገርም ነው። ስለዝኸ ስታወሪ ሰምቸሽም አላውቅ።”
ትናንት ፋሲለደስ ቤተመንግሥት ግቢ ስትገባ የነበራት የመደነቅ
ስሜት ኹሉ ጠፍቶባት ጭንቀት ያዛት። ለራሷ እኼ ቤተመንግሥት
ሚባል ነገር አስፈሪ ነው አለችና ወደ አልጋው ጫፍ አመራች።
ልብሶቹን በጥንቃቄ ወደ ኋላ ገፋ አድርጋ ተቀመጠች።
“ጌጦቹን አልጋው ላይ አኑሪያቸው” ብለው በቀኝ እጃቸው ኣልጋውን መታ አደረጉት።
“ልብሶቹን ደሞ እመንጠቆዎቹ ላይ ስቀያቸው” አሏት፣ ግድግዳ ላይ የተተከሉትን ከቀንድ የተሰሩ የልብስ መስቀያዎች
በእጃቸው እየጠቆሟት።
ጌጦቹን አልጋው ላይ ትታ ሄዳ ልብሶቹን አንድ በአንድ
ሰቀለቻቸውና ጫማዎቹን መሬት ላይ አስቀምጣ ተመልሳ አልጋው
ጫፍ ላይ ተቀመጠች።
“ምን እያልሽኝ ነበር? አዎ 'ስለዝህ ስታወሪ ሰምቸሽም አላውቅ
ነው ያልሽኝ” አለና፣ “ፊት ብታቂ ኑሮ ምን ይጠቅምሽ ኑሯል?
የዠመርሁትን ልጨርስልሽ እንጂ። ጃንሆይ እንዳልሁሽ በንጉሥ
ዮስጦስ ግዝየ ኸወህኒ አምባ ሲያመልጡ እኝሁ ዮስጦስ መልሰው አሰሯቸው። ያለቤታቸው ገብተው።”
“ያለቤታቸው ገብተው?”
“ዮስጦስ ማለት ልደታ ማርያምን እዝሁ እጐንደር የተከሉት
ያጤ ቴዎፍሎስ እንደራሴ ነበሩ እንጂ የነጋሢ ዘር የላቸውም። ኋላ
ጃንሆይ ደሞ ሲነግሡ ወህኒ አምባ ያሉ የነጋሢ ዝርያዎች ሁሉ የገዛ ወንድሞቻቸው ሳይቀሩ ተንጫጩ።”
“ምን ይሁን ብለው?”
“ሚነግሠውን እኛ እንመርጣለን፤ በካፋ ኃይለኛና ጨካኝ ነው
ብለው። ያው አልቀረም መሲሕ ሰገድ ተብለው ነገሡ። ይነግሣሉ ሚል ንግርትም ነበር። ጃንሆይ ወህኒ ሳሉ በሳቸው ልክ ጧሚና ጠሎተኛ አልነበረም ነው ሚሉ።
ምጥዋትም መስደድ ያዘወትሩ፣ መጻሕፍቱንም ያገላብጡ ነበር። ቅኔ አዋቂም ናቸው። ኸዛው እናታቸው አገር... ዲማ ነው ቅኔውን የተማሩ። ደሞ ምን የመሰለ ታንኳም አሠርተዋል እኮ።
ግብጦች ናቸው አሉ የሠሩላቸው። ኸጣና ነው ያለ...”
ድንገት ደንገጡሮቹ ሲገቡ ዝም አሉ። ሴቶቹ ወለተጊዮርጊስን
አልብሰው፣ አስጊጠውና እላይዋ ላይ ሽቱ አርከፍክፈው ግብር መታደሚያ ሰዐት ሲደርስ እንደሚመለሱና ግብር እንደ ንጉሠ ነገሥቱ ፍላጎትና
እንደ ሁኔታው የተለያየ አዳራሽ ውስጥ እንደሚደረግና ለዛሬ ግን ባለ ሁለት ደርቡ ወርቅ ሰቀላ ምድር ቤት አዳራሽ ውስጥ እንደሚሆን ነግረዋቸው ወጡ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
“ምንትዋብ ብያታለሁ።”
ወርቅ ሰቀላ ጥቁር እንግዳ ለመቀበል ዝግጁ ሆኗል። የእልፍኝ
አስከልካዩ በሥሩ ያሉትን እንደየደረጃቸው ነጠላ ያደገደጉትን፣ ወይም ካባ የደረቡትን ዐራቱን ጭፍሮቹን አሰማርቷል። ጠርዙ ባለወርቅ ቅብ
የሆነው የንጉሠ ነገሥቱ መንበረ መንግሥት የለበሰው የፋርስ ባለቀይ፣ባለሰማያዊና ባለነጭ ምንጣፍ በትክክል መነጠፉን፣ ከጎኑ ያለው ጠርዙ የወርቅ ቅብ የሆነው ድንክ አልጋ ዝግጁ መሆኑንና ከአልጋዎቹ ሥር
የተነጠፈው ቀይ የፋርስ ስጋጃ ላይ የሐር ምንጣፍ በትክክል መነጠፉን አረጋግጧል።
ከንጉሡ መንበር በስተጀርባ ያለውን ግድግዳ በቀይና በልዩ ልዩ
ቀለማት ያጌጠ ከቱርክ የመጣ ምንጣፍ ሸፍኖታል። ድንክ አልጋዎቹ የተቀመጡበትን አካባቢ ከሐር የተሠራ ነጭ አጎበር ከላይ ከልሎታል።አናቱ ላይ የዘውድ ቅርጽ ያለው ጉልላት ተቀምጦለታል። ንጉሠ
ነገሥቱ ሆኑ አብረዋቸው የሚቀመጡት እንግዶች እስኪገቡ አጎበሩ በግራና በቀኝ ያሉ እንጨቶች ላይ በቀጭን ሐር ሻሽ ታስሯል።ሲያስፈልግ የሚጋርዱትና የሚገልጡት ሁለት የቤተመንግሥት ባለሟሎች አደግድገው ግራና ቀኙን ቆመዋል። በአዳራሹ ግራና ቀኝ
ያሉ መስኮቶች የሐር መጋረጃ ተጋርደውባቸዋል።
👍18