#ውሉድ_ወወላድ
የወለደች ኹሉ . . .
እናት አትባልም! ግብሯ ካልተለየ ፤
የተወለደ ልጅ . . .
አይባልም ጧሪ!ምግባሩን ካለየ።
ዘር ስላካፈለ . . .
የአባት መኾን ክብር በከንቱ አይሰጥም!
ከልጅ ስም ቀጥሎ ስሙ አይቀመጥም!
እፍኝትን እይዋት .
እናት ትሞታለች ፣ ትውልድ ለማስቀጠል
አባትም ይሠዋል ፣በፍትወት መቃጠል።
አንበሳም ደቦሉን .
በጊዜው ካልቀጣ ንግሥናው ይቀማል ፤
የልጅነት ሥሥት ፣
የአባትነት ድርሻ ለክብር ይወድማል።
አዎ !
እናት ክብሯን ይዛ፣
ልጅ ግብሩን ተላብሶ ፣
አባት በስም ነግሦ፣
ካልተነጻጸረ፣
የመዳን ምሳሌው ትንቢቱ ተሻረ።
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
የወለደች ኹሉ . . .
እናት አትባልም! ግብሯ ካልተለየ ፤
የተወለደ ልጅ . . .
አይባልም ጧሪ!ምግባሩን ካለየ።
ዘር ስላካፈለ . . .
የአባት መኾን ክብር በከንቱ አይሰጥም!
ከልጅ ስም ቀጥሎ ስሙ አይቀመጥም!
እፍኝትን እይዋት .
እናት ትሞታለች ፣ ትውልድ ለማስቀጠል
አባትም ይሠዋል ፣በፍትወት መቃጠል።
አንበሳም ደቦሉን .
በጊዜው ካልቀጣ ንግሥናው ይቀማል ፤
የልጅነት ሥሥት ፣
የአባትነት ድርሻ ለክብር ይወድማል።
አዎ !
እናት ክብሯን ይዛ፣
ልጅ ግብሩን ተላብሶ ፣
አባት በስም ነግሦ፣
ካልተነጻጸረ፣
የመዳን ምሳሌው ትንቢቱ ተሻረ።
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘