#አረፍተ_ሀገር
“አበበ” ምንለው ፥ በሶ የሚበላ
ጩቤ እንደጨበጠ ፥ ለምናውቀው ጫላ
ጣሳ እያጠበ ፥ ለሚኖር ጨቡዴ
ሀገርሽ ሀገሬ
አረፍተ ነገርን ፥ ትመስላለች ውዴ።
*
ስልኬ አበበ ነው
በሶ ደሞ ካርዴ ፥ ስትገባኝ ሀገሬ
“ቴሌ ካርድ በላ።”
የሚል ትርጉም አለው ፣ አረፍተ ነገሬ።
*
ጫላ ባለ ስልጣን ፥ ስልጣን ደሞ ጩቤ
የጨበጡት ሁሉ
ሲያቆስሉት የኖሩ ፥ ስጋዬን ከልቤ።
***
ጨቡዴ ሙስና ፥ ጣሳ ደሞ ህዝቡ
እርቃን የሚያስቀሩት
በየ መሥሪያ ቤቱ ፥ ኪሱን እያሰቡ።
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
“አበበ” ምንለው ፥ በሶ የሚበላ
ጩቤ እንደጨበጠ ፥ ለምናውቀው ጫላ
ጣሳ እያጠበ ፥ ለሚኖር ጨቡዴ
ሀገርሽ ሀገሬ
አረፍተ ነገርን ፥ ትመስላለች ውዴ።
*
ስልኬ አበበ ነው
በሶ ደሞ ካርዴ ፥ ስትገባኝ ሀገሬ
“ቴሌ ካርድ በላ።”
የሚል ትርጉም አለው ፣ አረፍተ ነገሬ።
*
ጫላ ባለ ስልጣን ፥ ስልጣን ደሞ ጩቤ
የጨበጡት ሁሉ
ሲያቆስሉት የኖሩ ፥ ስጋዬን ከልቤ።
***
ጨቡዴ ሙስና ፥ ጣሳ ደሞ ህዝቡ
እርቃን የሚያስቀሩት
በየ መሥሪያ ቤቱ ፥ ኪሱን እያሰቡ።
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘