#ዜሮን_ፅፌ_አንድ_አለኝ
ሁለት ነው ልቤ!
አንድም ሞኝ ሲሆን ፤ አንድም ነው ወረቀት
አንድ የሚያደርጋቸው ፤ አለ አንድ ተረት
አለ አንዳች እውነት።
የያዙትን ነገር ፤ አይለቁም ሁለቱም
ዜሮን እየፃፉ
"አንድ አለኝ ይላሉ ፤ ሞኙም ወረቀቱም።
እኔ ካንቺ በፊት ፤ የማውቃቸው ሴቶች
ዛሬ ዜሮ ናቸው
ተፅፈው የቀሩ ፥ የሌሉ ስሌቶች።
ሔደዋል ብዙዎቹ ፤ በኔ እየተገፉ
አልፈዋል ብዙዎቹ ፤ እኔን እየገፉ
ዛሬ አንቺ ስትመጪ
በሞኝ ልቤ ላይ ፤ አኖርኩሽ አቅፌ
ለወረቀት ልቤ
"አንድ አለችኝ" አልኩት ፤ ዜሮዎቼን ፅፌ።
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
ሁለት ነው ልቤ!
አንድም ሞኝ ሲሆን ፤ አንድም ነው ወረቀት
አንድ የሚያደርጋቸው ፤ አለ አንድ ተረት
አለ አንዳች እውነት።
የያዙትን ነገር ፤ አይለቁም ሁለቱም
ዜሮን እየፃፉ
"አንድ አለኝ ይላሉ ፤ ሞኙም ወረቀቱም።
እኔ ካንቺ በፊት ፤ የማውቃቸው ሴቶች
ዛሬ ዜሮ ናቸው
ተፅፈው የቀሩ ፥ የሌሉ ስሌቶች።
ሔደዋል ብዙዎቹ ፤ በኔ እየተገፉ
አልፈዋል ብዙዎቹ ፤ እኔን እየገፉ
ዛሬ አንቺ ስትመጪ
በሞኝ ልቤ ላይ ፤ አኖርኩሽ አቅፌ
ለወረቀት ልቤ
"አንድ አለችኝ" አልኩት ፤ ዜሮዎቼን ፅፌ።
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘