#ቀላውጦ_ማስመለስ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሦስት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
በእርግጥ እናቴ እሷ መሆኗን እስካወቅኩበት ቀን ድረስ እናትና አባቴ ሞተውብኝ ከሩቅ ሀገር አምጥተው የሚያሳድጉኝ ጥያቄ አልባ
ቀኖች የነበሩኝ ህፃን ነበርኩ:: አባባ የምለው አሳዳጊዬ እግዚአብሔርን በመፍራቱና በደግነቱ ትንሿ ያደግኩባት የገጠር ከተማ ድፍን ነዋሪ የመሰከረለት፣ ሚስቱ የምትኮራበት፣ ልጆቹ የሚመፃደቁበት፣ እኔን ጨምሮ ቤቱ የምንኖር አገልጋዮቹ የምንመካበት ሰው ነበር፡፡ በልጅነቴ ውስጥ ያለው አሳዳጊዬ ይህ ነው፡፡ የልጅነትን ቡረቃ ተሰናብቼ መብሰልና ህልም ማለም ስጀምር ለክብሩ እንጂ ለእኔ ግድ ከሌለው አያቴ ጋር ተዋወቅን፡፡በእርግጥ በቸርነታቸው ከሚያሳድጉኝ መልካም አሳዳጊዎቼን
ላሳዩኝ በጎነት በልቤ የማመሰግን፣ ለውለታቸው ክፍያ በአቅሜ
የማገለግል አገልጋያቸው እንጂ ለጎደለው
የማማርርበት መብትም ሆነ ይገባኛል የምለው አንዳች ያልነበረኝ ትንሽዬ ልጅ ነበርኩ። ቢቆጡኝ፣ ቢሰድቡኝ፣ ቢያንቋሽሹኝ ትምህርት፣ ቢሰድቡኝ ትምህርት እንድማር ሳይፈቅዱልኝ ከማንበብና መፃፍ የዘለለ ባላውቅም፣ እንደልጅ ለመጫወት ባይፈቅዱልኝ
መሄጃ የለሽ ወላጅ አልባ ህፃን ለሚያሳድጉ ደግ አሳዳጊዎቼልክ ነገር መሆኑ ነበር የሚገባኝ፡፡
በአስራ አራት ዓመቴ ገደማ ለአዲስ ዓመት መለወጫ በዓል ሁሉም ቤተሰብ ተሰብስቧል። አክስቴና እሷ ከአዲስ አበባ ነበር የመጡት:: ሴትነቴ ያበበበት ወቅት ነው።የሰፈራችን ጎረምሶች
በአጠገቤ ሲያልፉ ቂጤን ገፍተር፣ ያጎጠጎጠ ጡቴን ቆንጠር እያደረጉ ያሽኮረምሙኛል፡፡ አመሻሹን ከብቶች ከሜዳ ይዤ ስመለስ ችፍ ያለው የሰንሰል ተክል አጠገብ አዳነ ቆሟል። ጎትቶ
ወደራሱ አስጠጋኝ፡፡ የመጀመሪያ ጊዜው አይደለም:: ጡቴን እንዳስነካው ያባብለኛል። ብዙ አላስለምነውም:: ሲነካካኝ ደስ ስለሚለኝ እፈቅድለታለሁ።
"እረፍ አዳነ ቤት ሁሉም አሉ። እየጠበቁኝ ነው ልቀቀኝ" ብዬው ነበር አልሰማኝም። እንደሌላ ቀኑ አላባበለኝም:: ወደ ሰንሰሉ
ውስጥ ይዞኝ ገባ፡፡ ከላዬ የለበስኩትን ልብስ ወደ ላይ ሰብስቦ ጡቴን ሲነካካኝ የምከለክልበት አቅምም ምክንያትም ከዳኝ። ሳሩ ላይ አጋድሞኝ ጡቴን በአፉ ሙሉ እየጎረሰ ሲተፋው እያቃሰትኩ
ነበር። ድንገት አቁሞ ሲበረግግ የጨፈንኳቸውን ዓይኖቼን ገለጥኳቸው።ያየሁትን ደግሜ ላለማየት ዓይኖቼን ጨፈንኳቸው። መልሼ አጮልቄ አየሁ። ከተጋደምኩበት ሆኜ ሳየው ጋሼ (የአባባ ብቸኛ ወንድ ልጅ) ከሰማይ ላይ ተወርውሮ የተንጠለጠለ መስሎ ዓይኑን ጎልጎሎ አፍጥጦብናል። አዳነ ፓንቱ እስኪቀደድ እግሬ አውጪኝ ብሎ ሲሮጥ ጋሼ ማጅራቴን ጨምድዶ ይዞኝ ወደቤት ገባ። በቤቱ ጣራ ስር ያሉትን ሁሉ
በጩኸቱ ስብስቦ እንደ ክፉ ወንጀለኛ ፊትለፊታቸው አቆመኝ፡፡የት እንዳገኘኝ እና ምን ስሰራ እንደነበረ በሚዘገንን ፀያፍ ቃል ለሁሉም ተናግሮ እንዳበቃ ተራ በተራ የምላሳቸውን መርዝ ተፉት። እሷ ምንም አልተናገረችም።ዓይኖቿ ውስጥ የነበረው መፀየፍ ግን ከእነርሱ ስድብ በላይ ህመም ነበረው።የሚያውቁትን ስድብና ቁጣ ሁላ ጨርሰው ፀጥ ሲሉ ወደ ጎዳ ገባሁ።እሷም ሲጋራዋን ልታጨስ ወደ ውጪ ወጣች።ጋሼም ተከተላት።በጎሮ በር አድርጌ ወጣሁ።ልሰማቸው ፈልጌ ባይሆንም ሲጯጯሁ ይሰማኛል። የመደናቆራቸው መንስኤ እኔ መሆኔን ሳውቅ ጆሮዬን ጥዬ መስማት ጀመርኩ፡፡
እንቺ የወረወርሻትን ዲቃላ እድሜ ለአባቴ በይ አሳደግንልሽ፡፡ እሷ ይዛብን የምትመጣውን ዲቃላ ማን ሊሸከምልሽ ነው?ካንቺም ብሶ እንዳለማች ቆጥረሽ ዝም ትያታለሽ? ባንቺ ነው የወጣችው! ገና ቂጧን ሳትጠርግ በየሳሩ ትሸረሙጣለች፡፡ ከዚህ በኋላ እግሯን እየጠበቅኩ የከፈተችውን እግሯን አልገጥምም።ከፈለግሽ ወስደሽ የምታደርጊውን አድርጊያት:: " ከእውነታው እኩል የመረጣቸው ፀያፍ ቃላት አስደነገጡኝ፡፡ የሰማሁት
እውነት መሆኑን መቀበል አቃተኝ፡፡ እሷ አትመልስለትም።አጎቴ አንዴ እህቱን አንዴ እኔን እየሞለጨ ደቂቃዎች አለፉ፡፡
ደጋግሞ ከተናገረው እሷ እናቴ መሆኗን እና ለእነሱ ጥላኝ እንደሄደች ገባኝ፡፡
"እናቴ አንቺ ነሽ? አባባ አያቴ ነው?" አልኩኝ ተኮራርፈው ሳሎን እንደተቀመጡ ሁሉም ነብር እንዳየ ጥንቸል ዓይናቸው
ተጎልጉሎ ጆሮአቸው ቆመ።የመለሰልኝ የለም፡፡
ውጪ ያወራችሁትን እንዳለ ሰምቻለሁ::" አልኳቸው፡፡
እና የሰማሽ እንደው ምን ይሁን? እኔ እናትሽ አይደለሁም ስትለኝ እናቴ መሆኗን ስሰማ ተንሰራፍቶ የነበረውን
ብልጭታ ደስታ በተነችው:: አጠገቧ ተጠግቼ እጇን ስይዛት መንጭቃ ገፈተረችኝ፡፡ እናቴ መሆኗን ሳላውቅም በፊት ይዣት አውቃለሁ፡፡ እንደዚህ አስጠልቻት አይቻት አላውቅም፡፡ እነ አባባ ጋር የምትመጣው ከስንት
ዓመት አንዴ ቢሆንም የምትለብሳቸው ልብሶች፣ ሲጋራ አጫጫሷ፣ ቁመቷ፣ አካሄዷ...
ባየኋት ቁጥር እንደርሷ መሆን የምመኝላት ነበረች::ስትመጣ እንግዳ ሲመጣ እንደማደርገው እግሯን የማጥባት እኔ ነበርኩ፡፡ ከስንት ዓመት አንዴ ለአዲስ ዘመን መለወጫ ስትመጣ
አዲስ ልብስ እቤት ላለነው ሁሉ ስትገዛ ለእኔም ገዝታልኝ ታውቃለች:: እንደዛ ቀን በጥላቻ አመናጭቃኝ አታውቅም።
በእርግጥ የምትፈልገውን ነገር ልታዝዘኝ ካልሆነ በቀር በፍቅር ወይ በክብርም አናግራኝ ማወቋን አላስታውስም፡፡
በደስታ፣በተስፋ እና ግራ በመጋባት መሃል ዋለልኩ:: በጥያቄ መዓት ተበታተንኩ፡፡ ተራ በተራ አፍ አፌን ብለው አባረሩኝ፡፡
ዓይኗን እንኳን መልሼ ሳላየው ተመልሳ ወደ አዲስ አበባ ሄደች።
ባልገባኝ ምክንያት ከዚያን ቀን በኋላ ከአባባ በቀር ሁሉም ያመናጭቀኝ ጀመር። ለምን የስጋቸው ክፋይ መሆኔ
እንዳሳፈራቸው ግራ ተጋባሁ:: ምንስ ቢሆን ደግሞ የእኔ ጥፋት ምኑ ላይ ነው? ከቀናት በኋላ አባባን እያለቀስኩ እውነቱን
እንዲነግረኝ ጠየቅኩት። የአስራ ሁለተኛ ክፍል ተማሪ ሳለች ከሆነ ጎረምሳ ጋር ተጣልታ ከባድ ጉዳት ስላደረሰችበት አስር ወር ተፈርዶባት መታሰሯን ነገረኝ። ማንም የተፈጠረውን አያውቅም፡፡ ሊጠይቋት ሲመላለሱ ማናቸውንም ለማግኘት ፈቃደኛ አልነበረችም። ፍርዷን ጨርሳ ወደ ቤት ስትመለስ መንገድ ላይ ነበር ምጥ የጀመራት:: ማናቸውም ማርገዟን ሳያውቁ እቤት እንደደረሰች ወለደችኝ፡፡ አባቷ ወግ አጥባቂ እና
ክብሩን ወዳድ ስለነበረ ተዋረድኩ ብሎ ያዙዙኝ ልቀቁኝ አለ፡፡
(ይሄን ሲነግረኝ በቁጭት ነበር) አንዲትም ቀን አላደረችም፡፡ለማንም ምንም ሳትል ከነደሜ ጥላኝ ጠፋች:: ከቤተሰቦቿ ጋር
መልሳ ስትገናኝ አድጌ በእግሬ ድክ ድክ እል ነበር። ሁሉም በዲቃላነቴ ደስተኛ ስላልነበሩ እናቴ መሆኗን እንዳላውቅ
የሰጠችው ማስጠንቀቂያ ተስማማቸው:: አብዛኛዎቹ የቤት አገልጋዮች እንደሚጠሩት ከስሜ የማስከትለው የአባባን ስም ነው:: የእኔ መወለድ ሌላ ሴት እንድትሆን እንዳደረጋት አባባ ሲነግረኝ ለቤተሰቡም ሆነ ለእናቴ ክፉ እጣ እንደሆንኩ ደጋገመልኝ እናቴ እኔን ከመውለዷ በፊት ከወንድ ልጁ ይልቅ በራስ መተማመኗ የሚያስተማምነው፣ ጎበዝ ተማሪ ስለነበረች ቤት ተከራይቶላት ከተማ የሚያስተምራት መኩሪያው፣ ትልቅ
ቦታ ትደርስልኛለች ብሎ የሚመካበት የዓይኑ ማረፊያ፣ ማንም ደፋር ቀና ብሎ የማያያት ጉልበተኛ እና ደፋር እንደነበረች
በትካዜ ፊቱ ደብዝዞ አወራኝ፡፡ እኔን ከወለደች በኋላ ጠፍታ ስትመለስ የማያውቋት ሌላ ሴት ሆና መምጣቷን ጨመረልኝ፡፡
"አባባ አባቴ ማን ነው?" አልኩት:: ምናልባት አባቴ ልጁን በፍቅር ክንዱን ሊዘረጋልኝ ይችላል ብዬ እያሰብኩ፡፡
"አናውቀውም:: ከእርሷ ውጪ የሚያውቅ የለም:: ስለአንቺም ሆነ ስለአባትሽ ጥያቄ ሲነሳባት ጣረሞት እንዳየ ሰው
ትንፈራገጣለች::” አለኝ፡፡
አባባ ከነገረኝ ያልተሟላ ታሪክ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሦስት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
በእርግጥ እናቴ እሷ መሆኗን እስካወቅኩበት ቀን ድረስ እናትና አባቴ ሞተውብኝ ከሩቅ ሀገር አምጥተው የሚያሳድጉኝ ጥያቄ አልባ
ቀኖች የነበሩኝ ህፃን ነበርኩ:: አባባ የምለው አሳዳጊዬ እግዚአብሔርን በመፍራቱና በደግነቱ ትንሿ ያደግኩባት የገጠር ከተማ ድፍን ነዋሪ የመሰከረለት፣ ሚስቱ የምትኮራበት፣ ልጆቹ የሚመፃደቁበት፣ እኔን ጨምሮ ቤቱ የምንኖር አገልጋዮቹ የምንመካበት ሰው ነበር፡፡ በልጅነቴ ውስጥ ያለው አሳዳጊዬ ይህ ነው፡፡ የልጅነትን ቡረቃ ተሰናብቼ መብሰልና ህልም ማለም ስጀምር ለክብሩ እንጂ ለእኔ ግድ ከሌለው አያቴ ጋር ተዋወቅን፡፡በእርግጥ በቸርነታቸው ከሚያሳድጉኝ መልካም አሳዳጊዎቼን
ላሳዩኝ በጎነት በልቤ የማመሰግን፣ ለውለታቸው ክፍያ በአቅሜ
የማገለግል አገልጋያቸው እንጂ ለጎደለው
የማማርርበት መብትም ሆነ ይገባኛል የምለው አንዳች ያልነበረኝ ትንሽዬ ልጅ ነበርኩ። ቢቆጡኝ፣ ቢሰድቡኝ፣ ቢያንቋሽሹኝ ትምህርት፣ ቢሰድቡኝ ትምህርት እንድማር ሳይፈቅዱልኝ ከማንበብና መፃፍ የዘለለ ባላውቅም፣ እንደልጅ ለመጫወት ባይፈቅዱልኝ
መሄጃ የለሽ ወላጅ አልባ ህፃን ለሚያሳድጉ ደግ አሳዳጊዎቼልክ ነገር መሆኑ ነበር የሚገባኝ፡፡
በአስራ አራት ዓመቴ ገደማ ለአዲስ ዓመት መለወጫ በዓል ሁሉም ቤተሰብ ተሰብስቧል። አክስቴና እሷ ከአዲስ አበባ ነበር የመጡት:: ሴትነቴ ያበበበት ወቅት ነው።የሰፈራችን ጎረምሶች
በአጠገቤ ሲያልፉ ቂጤን ገፍተር፣ ያጎጠጎጠ ጡቴን ቆንጠር እያደረጉ ያሽኮረምሙኛል፡፡ አመሻሹን ከብቶች ከሜዳ ይዤ ስመለስ ችፍ ያለው የሰንሰል ተክል አጠገብ አዳነ ቆሟል። ጎትቶ
ወደራሱ አስጠጋኝ፡፡ የመጀመሪያ ጊዜው አይደለም:: ጡቴን እንዳስነካው ያባብለኛል። ብዙ አላስለምነውም:: ሲነካካኝ ደስ ስለሚለኝ እፈቅድለታለሁ።
"እረፍ አዳነ ቤት ሁሉም አሉ። እየጠበቁኝ ነው ልቀቀኝ" ብዬው ነበር አልሰማኝም። እንደሌላ ቀኑ አላባበለኝም:: ወደ ሰንሰሉ
ውስጥ ይዞኝ ገባ፡፡ ከላዬ የለበስኩትን ልብስ ወደ ላይ ሰብስቦ ጡቴን ሲነካካኝ የምከለክልበት አቅምም ምክንያትም ከዳኝ። ሳሩ ላይ አጋድሞኝ ጡቴን በአፉ ሙሉ እየጎረሰ ሲተፋው እያቃሰትኩ
ነበር። ድንገት አቁሞ ሲበረግግ የጨፈንኳቸውን ዓይኖቼን ገለጥኳቸው።ያየሁትን ደግሜ ላለማየት ዓይኖቼን ጨፈንኳቸው። መልሼ አጮልቄ አየሁ። ከተጋደምኩበት ሆኜ ሳየው ጋሼ (የአባባ ብቸኛ ወንድ ልጅ) ከሰማይ ላይ ተወርውሮ የተንጠለጠለ መስሎ ዓይኑን ጎልጎሎ አፍጥጦብናል። አዳነ ፓንቱ እስኪቀደድ እግሬ አውጪኝ ብሎ ሲሮጥ ጋሼ ማጅራቴን ጨምድዶ ይዞኝ ወደቤት ገባ። በቤቱ ጣራ ስር ያሉትን ሁሉ
በጩኸቱ ስብስቦ እንደ ክፉ ወንጀለኛ ፊትለፊታቸው አቆመኝ፡፡የት እንዳገኘኝ እና ምን ስሰራ እንደነበረ በሚዘገንን ፀያፍ ቃል ለሁሉም ተናግሮ እንዳበቃ ተራ በተራ የምላሳቸውን መርዝ ተፉት። እሷ ምንም አልተናገረችም።ዓይኖቿ ውስጥ የነበረው መፀየፍ ግን ከእነርሱ ስድብ በላይ ህመም ነበረው።የሚያውቁትን ስድብና ቁጣ ሁላ ጨርሰው ፀጥ ሲሉ ወደ ጎዳ ገባሁ።እሷም ሲጋራዋን ልታጨስ ወደ ውጪ ወጣች።ጋሼም ተከተላት።በጎሮ በር አድርጌ ወጣሁ።ልሰማቸው ፈልጌ ባይሆንም ሲጯጯሁ ይሰማኛል። የመደናቆራቸው መንስኤ እኔ መሆኔን ሳውቅ ጆሮዬን ጥዬ መስማት ጀመርኩ፡፡
እንቺ የወረወርሻትን ዲቃላ እድሜ ለአባቴ በይ አሳደግንልሽ፡፡ እሷ ይዛብን የምትመጣውን ዲቃላ ማን ሊሸከምልሽ ነው?ካንቺም ብሶ እንዳለማች ቆጥረሽ ዝም ትያታለሽ? ባንቺ ነው የወጣችው! ገና ቂጧን ሳትጠርግ በየሳሩ ትሸረሙጣለች፡፡ ከዚህ በኋላ እግሯን እየጠበቅኩ የከፈተችውን እግሯን አልገጥምም።ከፈለግሽ ወስደሽ የምታደርጊውን አድርጊያት:: " ከእውነታው እኩል የመረጣቸው ፀያፍ ቃላት አስደነገጡኝ፡፡ የሰማሁት
እውነት መሆኑን መቀበል አቃተኝ፡፡ እሷ አትመልስለትም።አጎቴ አንዴ እህቱን አንዴ እኔን እየሞለጨ ደቂቃዎች አለፉ፡፡
ደጋግሞ ከተናገረው እሷ እናቴ መሆኗን እና ለእነሱ ጥላኝ እንደሄደች ገባኝ፡፡
"እናቴ አንቺ ነሽ? አባባ አያቴ ነው?" አልኩኝ ተኮራርፈው ሳሎን እንደተቀመጡ ሁሉም ነብር እንዳየ ጥንቸል ዓይናቸው
ተጎልጉሎ ጆሮአቸው ቆመ።የመለሰልኝ የለም፡፡
ውጪ ያወራችሁትን እንዳለ ሰምቻለሁ::" አልኳቸው፡፡
እና የሰማሽ እንደው ምን ይሁን? እኔ እናትሽ አይደለሁም ስትለኝ እናቴ መሆኗን ስሰማ ተንሰራፍቶ የነበረውን
ብልጭታ ደስታ በተነችው:: አጠገቧ ተጠግቼ እጇን ስይዛት መንጭቃ ገፈተረችኝ፡፡ እናቴ መሆኗን ሳላውቅም በፊት ይዣት አውቃለሁ፡፡ እንደዚህ አስጠልቻት አይቻት አላውቅም፡፡ እነ አባባ ጋር የምትመጣው ከስንት
ዓመት አንዴ ቢሆንም የምትለብሳቸው ልብሶች፣ ሲጋራ አጫጫሷ፣ ቁመቷ፣ አካሄዷ...
ባየኋት ቁጥር እንደርሷ መሆን የምመኝላት ነበረች::ስትመጣ እንግዳ ሲመጣ እንደማደርገው እግሯን የማጥባት እኔ ነበርኩ፡፡ ከስንት ዓመት አንዴ ለአዲስ ዘመን መለወጫ ስትመጣ
አዲስ ልብስ እቤት ላለነው ሁሉ ስትገዛ ለእኔም ገዝታልኝ ታውቃለች:: እንደዛ ቀን በጥላቻ አመናጭቃኝ አታውቅም።
በእርግጥ የምትፈልገውን ነገር ልታዝዘኝ ካልሆነ በቀር በፍቅር ወይ በክብርም አናግራኝ ማወቋን አላስታውስም፡፡
በደስታ፣በተስፋ እና ግራ በመጋባት መሃል ዋለልኩ:: በጥያቄ መዓት ተበታተንኩ፡፡ ተራ በተራ አፍ አፌን ብለው አባረሩኝ፡፡
ዓይኗን እንኳን መልሼ ሳላየው ተመልሳ ወደ አዲስ አበባ ሄደች።
ባልገባኝ ምክንያት ከዚያን ቀን በኋላ ከአባባ በቀር ሁሉም ያመናጭቀኝ ጀመር። ለምን የስጋቸው ክፋይ መሆኔ
እንዳሳፈራቸው ግራ ተጋባሁ:: ምንስ ቢሆን ደግሞ የእኔ ጥፋት ምኑ ላይ ነው? ከቀናት በኋላ አባባን እያለቀስኩ እውነቱን
እንዲነግረኝ ጠየቅኩት። የአስራ ሁለተኛ ክፍል ተማሪ ሳለች ከሆነ ጎረምሳ ጋር ተጣልታ ከባድ ጉዳት ስላደረሰችበት አስር ወር ተፈርዶባት መታሰሯን ነገረኝ። ማንም የተፈጠረውን አያውቅም፡፡ ሊጠይቋት ሲመላለሱ ማናቸውንም ለማግኘት ፈቃደኛ አልነበረችም። ፍርዷን ጨርሳ ወደ ቤት ስትመለስ መንገድ ላይ ነበር ምጥ የጀመራት:: ማናቸውም ማርገዟን ሳያውቁ እቤት እንደደረሰች ወለደችኝ፡፡ አባቷ ወግ አጥባቂ እና
ክብሩን ወዳድ ስለነበረ ተዋረድኩ ብሎ ያዙዙኝ ልቀቁኝ አለ፡፡
(ይሄን ሲነግረኝ በቁጭት ነበር) አንዲትም ቀን አላደረችም፡፡ለማንም ምንም ሳትል ከነደሜ ጥላኝ ጠፋች:: ከቤተሰቦቿ ጋር
መልሳ ስትገናኝ አድጌ በእግሬ ድክ ድክ እል ነበር። ሁሉም በዲቃላነቴ ደስተኛ ስላልነበሩ እናቴ መሆኗን እንዳላውቅ
የሰጠችው ማስጠንቀቂያ ተስማማቸው:: አብዛኛዎቹ የቤት አገልጋዮች እንደሚጠሩት ከስሜ የማስከትለው የአባባን ስም ነው:: የእኔ መወለድ ሌላ ሴት እንድትሆን እንዳደረጋት አባባ ሲነግረኝ ለቤተሰቡም ሆነ ለእናቴ ክፉ እጣ እንደሆንኩ ደጋገመልኝ እናቴ እኔን ከመውለዷ በፊት ከወንድ ልጁ ይልቅ በራስ መተማመኗ የሚያስተማምነው፣ ጎበዝ ተማሪ ስለነበረች ቤት ተከራይቶላት ከተማ የሚያስተምራት መኩሪያው፣ ትልቅ
ቦታ ትደርስልኛለች ብሎ የሚመካበት የዓይኑ ማረፊያ፣ ማንም ደፋር ቀና ብሎ የማያያት ጉልበተኛ እና ደፋር እንደነበረች
በትካዜ ፊቱ ደብዝዞ አወራኝ፡፡ እኔን ከወለደች በኋላ ጠፍታ ስትመለስ የማያውቋት ሌላ ሴት ሆና መምጣቷን ጨመረልኝ፡፡
"አባባ አባቴ ማን ነው?" አልኩት:: ምናልባት አባቴ ልጁን በፍቅር ክንዱን ሊዘረጋልኝ ይችላል ብዬ እያሰብኩ፡፡
"አናውቀውም:: ከእርሷ ውጪ የሚያውቅ የለም:: ስለአንቺም ሆነ ስለአባትሽ ጥያቄ ሲነሳባት ጣረሞት እንዳየ ሰው
ትንፈራገጣለች::” አለኝ፡፡
አባባ ከነገረኝ ያልተሟላ ታሪክ
👍2
በመነሳት እናቴ የሴት ልጅ ዶክተር፣ ኢንጂነር፣ ሊቅ........ መሆን በሚደንቃት ትንሽዬ
መንደራቸው ከእኩዮቿ በተለየ ከህፃንነቷ ጀምሮ ዩንቨርስቲ ገብታ በማዕረግ የመመረቅ ህልም የነበራት የመንደሯ ፈርጥ ነበረች:: ህልሟን ለመጨበጥ መንገዷን ስታገባድድ እኔ በመንገዷ ገባሁ:: እኔን ለመውለድ ምን ዓይነት ስቃይ እንዳለፈች ከእሷና ከፈጣሪ ውጪ አውቃለሁ የሚል ባይኖርም ለእናቴ የሳቋ
ሞት፣ የተስፋዋ መቁረጥ፣ የብርታቷ መድቀቅ፣ ግብ አልባ መናኛ ሴት የመሆኗ ጅማሬ እኔ መሆኔ ገባኝ፡፡ እኔን ተጠያቂ የሚያደርገኝ ግን የትኛው ድርጊቴ ነው? ከአባባ ጋር ካወራሁ በኋላ የበፊቷን ራሴን መሆን አቃተኝ፡፡የሚያሳዩኝ ጠጠር ንቀት
ቋጥኝ ያክልብኛል። ከቤተሰብ እንደአንዷ ሊቆጥሩኝ ያለመቻላቸው እንደ ተራራ የገዘፈ ጥላቻ ይሆንብኛል። እየታየ
የመጣ ሴትነቴን ተከትሎ ከሰፈሩ ጎረምሳ ሁላ ጋር ባልዋልኩበት እያጋደሙኝ የሚለጥፉብኝ ፀያፍ ስድብ አንገቴን ወደ መሬት ቀለበሰው:ፈ። አባባጋ አዘውትሮ የሚመላለስ የቡና ነጋዴ ሊያገባኝ
ሲጠይቃቸው ሸክማቸውን እንደገላገላቸው ቆጥረው ሳይነግሩኝ ተስማሙ። ደስ ይበለኝ ወይ ልዘን ግድ
አልሰጣቸውም:: በራሴ ላይ እንኳን ስልጣን የሌለኝ መሆኔን ሲመሰክሩልኝ የጉዳዩዋ ባለቤት ሳላውቅ በእኔ ልዋጭ ከብትና ገንዘብ ተሰጣቸው። በተለመደ ቀኔ ውስጥ እቃ አድርሺ ተብዬ ያልተለመደ ትዕዛዝ ታዘዝኩ:: አንድ ቀን ከአባባ ጋር የሄድንበት የሰውየው ዘመዶች ቤት ነበር፡፡ ሰውየው ጋ በተላኩበት ይዞኝ ወደ አዲስ አበባ መጣ። ከማላውቀው ሰው ጋር አልተኛም
ባልኩኝ እንደጥጋበኛ ተቆጥሬ ጉንጩ በጥፊ ቀላ፡ ከተፈሪ ጋር መኖር በጀመርኩ በቀናት ውስጥ ጠፍቼ አባባ ጋር ተመለስኩ፡፡መጠለፌን ስነግራቸው ሳቁብኝ፡፡ በስሜቴ፣ በገላዬ፣ በወደፊቴ፣
በፍላጎቴ እነሱ ከጀርባዬ ተስማምተው መጨረሳቸውን የሰማሁት ይሄኔ ነበር።
የተሰበረ መንፈሴን መጠገኛ አጣሁ:: ይባስ ብሎ አቶ ተፈሪ ለአባባ ወቀሳ መላኩን ስሰማ ራሴን፣ ሴት መሆኔን፣ ሰው
መሆኔንም ጠላሁት፡፡የተበደልኩ እኔ የሚደራደሩት እነሱ።ያለፍላጎቴ እንደደፈረኝ ለአባባ ህመሜን በእንባ መንገሬ ለእሱ የካሳ ምንጩ መሆኑ ደግሞ የማይድን ድንዝና በልቤ ውስጥ
ረጨብኝ፡፡ ልጅነቴ ሳያሳሳው የፈነጨብኝ እኔ የሚካሱት ቤተሰቦቼ፣ የተበደልኩ እኔ አቤቱታው የሚሰማው የሱ፣የተሰበርኩ እኔ ስለደፈረኝ እኔ የምሸለመው ለሱ:: ለደንብ ያህል ሽማግሌ ተሰብስቦ በፈጣሪ ቃል፣በባህልና ወግ፣ በትህምክታቸው እና በእርባና ቢስነቴ እያመኻኙ በደሌን እንኳን ሳይሰሙ እኔው
ለተበደልኩ ይቅርታ መጠየቅ ግዴታዬ ሆነ፡፡ እናቴስ ልጇን የክዳችኝ ምንም ይሁን ምን ምክንያት ሊኖራት ይችላል ብዬ ላስብ ምናልባትም ክፉ ስለሆነች ነው ብዬም ልመን እንዴት ከቤተሰቤ ሁሉ ለለቅሶዬ ጆሮ የሚሰጥ አንድ አጣለሁ? እዚህኛው የጥያቄ ወለል ላይ ስቆም ነው የሽክርክሪቴ መሀለኛ ነጥብ እሷ መሆኗ የተገለጠልኝ፡፡........
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
መንደራቸው ከእኩዮቿ በተለየ ከህፃንነቷ ጀምሮ ዩንቨርስቲ ገብታ በማዕረግ የመመረቅ ህልም የነበራት የመንደሯ ፈርጥ ነበረች:: ህልሟን ለመጨበጥ መንገዷን ስታገባድድ እኔ በመንገዷ ገባሁ:: እኔን ለመውለድ ምን ዓይነት ስቃይ እንዳለፈች ከእሷና ከፈጣሪ ውጪ አውቃለሁ የሚል ባይኖርም ለእናቴ የሳቋ
ሞት፣ የተስፋዋ መቁረጥ፣ የብርታቷ መድቀቅ፣ ግብ አልባ መናኛ ሴት የመሆኗ ጅማሬ እኔ መሆኔ ገባኝ፡፡ እኔን ተጠያቂ የሚያደርገኝ ግን የትኛው ድርጊቴ ነው? ከአባባ ጋር ካወራሁ በኋላ የበፊቷን ራሴን መሆን አቃተኝ፡፡የሚያሳዩኝ ጠጠር ንቀት
ቋጥኝ ያክልብኛል። ከቤተሰብ እንደአንዷ ሊቆጥሩኝ ያለመቻላቸው እንደ ተራራ የገዘፈ ጥላቻ ይሆንብኛል። እየታየ
የመጣ ሴትነቴን ተከትሎ ከሰፈሩ ጎረምሳ ሁላ ጋር ባልዋልኩበት እያጋደሙኝ የሚለጥፉብኝ ፀያፍ ስድብ አንገቴን ወደ መሬት ቀለበሰው:ፈ። አባባጋ አዘውትሮ የሚመላለስ የቡና ነጋዴ ሊያገባኝ
ሲጠይቃቸው ሸክማቸውን እንደገላገላቸው ቆጥረው ሳይነግሩኝ ተስማሙ። ደስ ይበለኝ ወይ ልዘን ግድ
አልሰጣቸውም:: በራሴ ላይ እንኳን ስልጣን የሌለኝ መሆኔን ሲመሰክሩልኝ የጉዳዩዋ ባለቤት ሳላውቅ በእኔ ልዋጭ ከብትና ገንዘብ ተሰጣቸው። በተለመደ ቀኔ ውስጥ እቃ አድርሺ ተብዬ ያልተለመደ ትዕዛዝ ታዘዝኩ:: አንድ ቀን ከአባባ ጋር የሄድንበት የሰውየው ዘመዶች ቤት ነበር፡፡ ሰውየው ጋ በተላኩበት ይዞኝ ወደ አዲስ አበባ መጣ። ከማላውቀው ሰው ጋር አልተኛም
ባልኩኝ እንደጥጋበኛ ተቆጥሬ ጉንጩ በጥፊ ቀላ፡ ከተፈሪ ጋር መኖር በጀመርኩ በቀናት ውስጥ ጠፍቼ አባባ ጋር ተመለስኩ፡፡መጠለፌን ስነግራቸው ሳቁብኝ፡፡ በስሜቴ፣ በገላዬ፣ በወደፊቴ፣
በፍላጎቴ እነሱ ከጀርባዬ ተስማምተው መጨረሳቸውን የሰማሁት ይሄኔ ነበር።
የተሰበረ መንፈሴን መጠገኛ አጣሁ:: ይባስ ብሎ አቶ ተፈሪ ለአባባ ወቀሳ መላኩን ስሰማ ራሴን፣ ሴት መሆኔን፣ ሰው
መሆኔንም ጠላሁት፡፡የተበደልኩ እኔ የሚደራደሩት እነሱ።ያለፍላጎቴ እንደደፈረኝ ለአባባ ህመሜን በእንባ መንገሬ ለእሱ የካሳ ምንጩ መሆኑ ደግሞ የማይድን ድንዝና በልቤ ውስጥ
ረጨብኝ፡፡ ልጅነቴ ሳያሳሳው የፈነጨብኝ እኔ የሚካሱት ቤተሰቦቼ፣ የተበደልኩ እኔ አቤቱታው የሚሰማው የሱ፣የተሰበርኩ እኔ ስለደፈረኝ እኔ የምሸለመው ለሱ:: ለደንብ ያህል ሽማግሌ ተሰብስቦ በፈጣሪ ቃል፣በባህልና ወግ፣ በትህምክታቸው እና በእርባና ቢስነቴ እያመኻኙ በደሌን እንኳን ሳይሰሙ እኔው
ለተበደልኩ ይቅርታ መጠየቅ ግዴታዬ ሆነ፡፡ እናቴስ ልጇን የክዳችኝ ምንም ይሁን ምን ምክንያት ሊኖራት ይችላል ብዬ ላስብ ምናልባትም ክፉ ስለሆነች ነው ብዬም ልመን እንዴት ከቤተሰቤ ሁሉ ለለቅሶዬ ጆሮ የሚሰጥ አንድ አጣለሁ? እዚህኛው የጥያቄ ወለል ላይ ስቆም ነው የሽክርክሪቴ መሀለኛ ነጥብ እሷ መሆኗ የተገለጠልኝ፡፡........
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
#ምህረትህን_መልበሴን
"ባዝኖ! ባዝኖ! ባዝኖ!
ዋትቶ! ዋትቶ! ዋትቶ!
በጭጋጋማው ቀን
በደመናው ሞቶ
'ርቃኑን ተቀብሯል"
ብለው ያወራሉ
ም'ረትኸን መልበሴን
የማያውቁ ሁሉ።
"ባዝኖ! ባዝኖ! ባዝኖ!
ዋትቶ! ዋትቶ! ዋትቶ!
በጭጋጋማው ቀን
በደመናው ሞቶ
'ርቃኑን ተቀብሯል"
ብለው ያወራሉ
ም'ረትኸን መልበሴን
የማያውቁ ሁሉ።
#ቀላውጦ_ማስመለስ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
እኔ ለተበደልኩ ይቅርታ መጠየቅ ግዴታዬ ሆነ፡፡ እናቴስ ልጇን የክዳችኝ ምንም ይሁን ምን ምክንያት ሊኖራት ይችላል ብዬ ላስብ ምናልባትም ክፉ ስለሆነች ነው ብዬም ልመን እንዴት ከቤተሰቤ ሁሉ ለለቅሶዬ ጆሮ የሚሰጥ አንድ አጣለሁ? እዚህኛው የጥያቄ ወለል ላይ ስቆም ነው የሽክርክሪቴ መሀለኛ ነጥብ እሷ መሆኗ የተገለጠልኝ፡፡
የታየኝ ጭላንጭል ብልጭታ እናቴጋ መሄድ ነበር፡፡ እናቴ መሆኗ ባያራራት እንኳን ሴት መሆኗ ለስሜቴ ቅርብ
ያደርጋታል ብዬ አመንኩ፡፡ በግዳጅ ተመልሼ ከገባሁበት የተፈሪ ቤት ጠፍቼ እናቴን ለማግኘት ሻንጣዬን ይዤ ወጣሁ። የህይወቴ ሰንካላ ሽክርክሪት መጀመሪያው ይህ ጉዞዬ መሆኑ የገባኝ
ሰነባብቶ ነበር፡፡ ተደብቄ ከአጎቴ ማስታወሻ ደብተር ላይ የገለበጥኩት የቤቷ ስልክ ቁጥር ላይ ደወልኩ፡፡ የነፃነቴ ቁልፍ፣የምስቅልቅሌ ፍቺ፣ የኑረቴ አዲስ ምዕራፍ፣ ዳግም ውልደቴ እሷ መሆኗን እየቃዠሁ በጉጉት ተሰቅዤ አገኘኋት። ከቅዠቴ ለመንቃት ደቂቃዎች በቂ ነበሩ፡፡ ያገኘችኝ ቦታ ጥላኝ አልሄደችም:: ወደ ቤቷ ወሰደችኝ፡፡ ባሏና የእንጀራ ልጇ መሆናቸውን ከነገረችኝ ወንዶች ጋር የቅብጠት ኑሮ ነበር የምትኖረው። ያላቸው ትስስር ጥብቀት ምን ያህል የተገመደ መሆኑን ባላውቅም አብሯት በሚኖረው የእንጀራ ልጇ ቀናሁ።
ስለእናቴ ልጠይቀው ተመኘሁ። ግን እድሉን አላገኘሁም።በእርግጥ ልጇ መሆኔን ለአንዳቸውም መንገሯን
እጠራጠራለሁ።ልጁ አብሯቸው ቢኖርም ብቸኛ ይመስላል፡፡ቤታቸው ውስጥ ለጊዜው ትኩረት ልሰጠው ያልፈለግኩት የሆነ ልክ ያልሆነ ነገር እንዳለ ተሰምቶኛል፡፡
ምን ልታደርጊ መጣሽ?" ስትለኝ ፊቷ ላይ የነበረው መሸከክ ቢያስደነግጠኝም ምክንያቴን እስክነግራት ነው
ብዬ ራሴን አበረታሁ። የሆንኩትን ሁሉ ከዓይኔ የሚፈሰውን እንባና የአፍንጫዬን ንፍጥ በእጄ አይበሉባ እየሞዠቅኩ ነገርኳት።
"እና? እከክሽን እያከክሽ ከመኖር አይሻልሽም? ወይስ እድሜ ልክሽን በየአውድማው ከጎረምሳ ጋር እየተላፋሽ መኖር ነው የምትፈልጊው? ዝቀሽ የማትጨርሺው ሀብት ላይ ስለጣለሽ
ልታመሰግኚው ሲገባ አባቴን የምትኮንኚው ምን አድርግ ብለሽ
ነው?" ነበር ለለቅሶዬና ለብሶቴ መልሷ። ከዚህ በላይ ልትሰማኝ አንድ ደቂቃ አላባከነችም። በሚቀጥለው ቀን ተመልሼ ባሌ ያደረጉት ተፈሪጋ ለመሄድ እንድስናዳ ነገረችኝ፡፡
"እርሺው እኔ እስከዛሬ እናትሽ እንዳልነበርኩ ሁሉ ከዚህ በኋላም
እናትሽ ልሆን አልችልም።ሰበብ እየፈለግሽ ልታገኚኝ እንዳትሞክሪ።" የሚል ማስጠንቀቂያ አከለችበት። የተሰማኝ ስሜት አልነበረም።ምክንያቱም ደንዝዣለሁ። ከተቀመጥኩበት
ለመነሳት ሰውነቴ እንደወትሮው የሚታጠፍ የሚዘረጋ እስከማይመስለኝ በድኛለሁ። በጠዋት የቀሰቀሰችኝ የትራንስፖርት ገንዘብ ሰጥታኝ ከቤቷ ልታሰናብተኝ ነበር፡፡ለቀናት የማደርገውን ሁሉ የማደርገው አስቤ አልነበረም።
መላው አካሌ ከጭንቅላቴ ጋር እየተማከረ መንቀሳቀሱን እንጃ፡፡ ራሴን ከተፈሪ ጋር ያለኝን ኑሮ እያለማመድኩት አገኘሁት።ብቸኛው ፍቅርን ሊያሳየኝ የሚሞክር ፍጡር እሱ ነው።እውነቱን ነው ግን? እያልኩ አስባለሁ። ስለ ወለደችኝ ሴት ከማሰብ የላቀ የምሰራው የዛሬም ሆነ የነገ እቅድ ስላልነበረኝ እሱ የሚያቅድልኝን ውሎ እውላለሁ። መኪና መንዳት መማር፣የምግብ አሰራር ስልጠና ሙያ መሰልጠን፣ ከጓደኞቹ ሚስቶች
ጋር ተማክሮ ገዝቶ በሚያመጣልኝ ልብስና ጫማ ራሴን ለእርሱ ማስጌጥ፣ ፀጉሬን መሰራት እንዳለብኝ አሳስቦኝ በወጣ ቀን ጠዋት የራስ ቅሌን ለፀጉር ሰሪዎቹ እጅ መስጠት፣ ሊተኛኝ ፈልጎ ሲያላዝን በጀርባዬ ተጋድሜ እግሮቼን መክፈት፣በስራ ሰበብ ሲወሰልት ያደረ ቀን በጠዋት ገዝቶ የሚመጣው በግ መስራት.....(አይነግረኝም።አውቃለሁ።
እንደማውቅ ያውቃል።መፀፀቱን አያቆምም።መወስለቱንም እንደዛው። ከሌላ ሴት ጋር ማደሩን ማወቄ ግድ አይሰጠኝም ነበር፡፡ ምናልባት ለእርሱ ግድ ስለሌለኝ አልያም ለራሴ ግድ
ስለሌለኝ ወይ ደግሞ በሆነች የሀሳቤ ጥግ ሌላ ሴት ለመፈለጉ ምክንያት የራሴ መበደን መቀበሌ ይሆናል የዓመታት ባሌ ከሌላ ሴት ጋር በማደሩ ለሚሰማው ፀፀት ማስተሰሪያ የበግ ደም ማፍሰሱን መቀበሌ።)
በራሷ ጭንቅላት የምታስብ ሴት መሆኔ ጠፍቶ በተፈሪ ባወጣልኝ የእለት መመሪያ የምንቀሳቀስ ሮቦት ለመሆን የፈጀብኝ
ጥቂት ወራት ነው። ተፈሪ በስራው ምክንያት ከከተማ እስካልወጣ ድረስ ቀላል ግልፅ እና ተመሳሳይ የአስራ ስድስት ዓመት ውሎ...
የሚወደውን ምግብ ማብሰል፣ ሱቅ ወጥቶ የሚያስፈልግ ነገር መገዛዛት፣ እሱ እንድሆንለት የሚፈልጋትን ንፁህና ዘናጭ ሴት ሆኜ መጎለት፣ እላዬ ላይ ራቁቱን
እየተወዛወዘ መቼ ልጅ እንደምወልድለት ሲነዛነዝ መስማት፡፡
በራሴ ጭንቅላት የማደርገው ብቸኛ ነገር ለእናቴ ስልክ እየደወልኩ በስልኩ ሞገድ ድንዛዜን ማጨድ ብቻ ነው:: የተለየ
ነገር ከአፏ እንዲወጣ በመናፈቅ ሳልታክት ደውልላታለሁ።ከሚቆጠሩ ቃላት የዘለለ አታናግረኝም። ለምጠይቃት ጥያቄ
መልስ አትመልስልኝም። ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ባሏ ነኝ ያለ ሰውዬ በዚያ ስልክ እንደማላገኛት ነገረኝ፡፡ ደጋግሜ ብደውልም መልሱ ተመሳሳይ ነበር፡፡ የሆነ እለት እንደአበደ ሰው ተነስቼ
ቤቷ ሄድኩ፡፡ ከቤቷ ከወጣች መሰንበቷን ባሏ የነበረው ሰው እየተነጫነጨ ነገረኝ። የት መሆኗን ሊነግረኝ አልፈለገም ከብዙ ወራት በኋላ በተለመደ ውሎዬ መሃከል ያልተለመደ ስልክ ጥሪ አስተናገድኩ፡፡ አባባ ነበረ። ድምፁን ስሰማ እስከዛ ቀን ድረስ ደህንነቴ ወይ ምቾቴ ግድ ሰጥቶት ደውሉልኝ አለማወቁን እረስቼ ናፍቆቴን ገለፅኩለት: የአቧራ ብናኝ ያህል ግድ
አልሰጠውም:: የእናቴ ባል ስለሞተ ለቅሶ እንድደርስ ነገረኝ። ሟች ባሏ ድጋሚ እሷን ለማየት ምክንያት ስለሆነኝ መሞቱ
አስፈነደቀኝ፡፡ ከተፈሪ ጋር ለቅሶ ለመድረስ ሄድን፡፡ ዘመዶቼ ለቅሶውን የነገረኝ አባባን ጨምሮ ማንም ያለመምጣታቸው
አስገረመኝ፡፡ ድንኳኑ ውስጥ ለሟች ባሏ አምርራ ስታለቅስ ሳያት ድፍርስርስ ያለ ስሜት ተሰማኝ፡፡ ለባሏ ስትነፋረቅ ሳያት
ቅናት አነደደኝ፡፡ ለደንዳና ልቧ የሰጠሁት አንዱ ማስተባበያዬ ፉርሽ ሆነብኝ፡፡ ለአፍታ ተፈጥሮዋ ድንጋይነት እንደሆነ ሳምን መሰንበቴ ተሰረዞ ሌላ ነገር የገባኝ መሰለኝ፡፡ ሴትየዋ ከኔ ውጪ
ላለ ሰው ልቧ ስጋ እና ደም ነው ብዬ አሰብኩ፡፡ የሟች ልጅ ነው ያለችኝ ወጣት በአባቱ ሞት ያዘነ አይመስልም። እንደታዛቢ ለቀስተኛውን ይገረምማል:: አመሻሹን የለቅሶ ግርግር ሲበርድ
ጠብቄ ባገኘኋት ስንጣቂ አጋጣሚ ተጠቅሜ እያቀፍኳት ምን ያህል እንዳዘንኩ የልቧ በራፍ ያስጠጋኛል
ብዬ በተለማመድኳቸው ቃላት ነገርኳት። ለደቂቃ በእውነታ የሌለሁ የምቃዥ መሰለኝ፡፡ መልሳ አቅፋኝ አመሰገነችኝ፡፡ ካገባሁት ለመጀመሪያ ጊዜ ከተፈሪ ጋር እንደቅርብ ሰው ስለእርሷ እቅፍ
ንዝረት አብራራሁለት:: ከድንኳኑ ይዤው ወጥቼ ስለእኔ የማያውቀውን ታሪክ በደስታ እየፈነደቅኩ ነገርኩት፡፡ በደሜ
የሚንቀለቀለው እሳት የገባው መሰለኝ:: ባይገባውም ግድ አልነበረኝም። እናቴ ባቀፈችኝ በዛች ደቂቃ ዓለም ቀጥ ብላ
የተፈጥሮ ዑደቶች “ሀ” ብለው አዲስ ቀመር መቀመር እንደጀመሩ ነው የተሰማኝ፡፡ ደስታዬ የተጋባበት መሰለ። ወደ ድንኳኑ ስንመለስ ጨለማው ውስጥ የሳቅ ድምፅ የሰማሁ መሰለኝ፡፡ ምን አስቤ እንደሆነ አላውቅም ተፈሪን በቆመበት ትቼው ወደ ሰማሁት ድምፅ ተራመድኩ፡፡ እናቴ ናት፡፡ ቅድም የነፍስ አባቷ መሆኑን ሲያወሩ ከሰማሁት ሰው ጋር ጨለማው ውስጥ እየተላፉ ይሳሳቃሉ። የነፍስ አባቷ አፉን ድንቅፍ እንኳን አይለው ከሟች በመገላገላቸው የጀመሩትን የድብቅ ፍቅር
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
እኔ ለተበደልኩ ይቅርታ መጠየቅ ግዴታዬ ሆነ፡፡ እናቴስ ልጇን የክዳችኝ ምንም ይሁን ምን ምክንያት ሊኖራት ይችላል ብዬ ላስብ ምናልባትም ክፉ ስለሆነች ነው ብዬም ልመን እንዴት ከቤተሰቤ ሁሉ ለለቅሶዬ ጆሮ የሚሰጥ አንድ አጣለሁ? እዚህኛው የጥያቄ ወለል ላይ ስቆም ነው የሽክርክሪቴ መሀለኛ ነጥብ እሷ መሆኗ የተገለጠልኝ፡፡
የታየኝ ጭላንጭል ብልጭታ እናቴጋ መሄድ ነበር፡፡ እናቴ መሆኗ ባያራራት እንኳን ሴት መሆኗ ለስሜቴ ቅርብ
ያደርጋታል ብዬ አመንኩ፡፡ በግዳጅ ተመልሼ ከገባሁበት የተፈሪ ቤት ጠፍቼ እናቴን ለማግኘት ሻንጣዬን ይዤ ወጣሁ። የህይወቴ ሰንካላ ሽክርክሪት መጀመሪያው ይህ ጉዞዬ መሆኑ የገባኝ
ሰነባብቶ ነበር፡፡ ተደብቄ ከአጎቴ ማስታወሻ ደብተር ላይ የገለበጥኩት የቤቷ ስልክ ቁጥር ላይ ደወልኩ፡፡ የነፃነቴ ቁልፍ፣የምስቅልቅሌ ፍቺ፣ የኑረቴ አዲስ ምዕራፍ፣ ዳግም ውልደቴ እሷ መሆኗን እየቃዠሁ በጉጉት ተሰቅዤ አገኘኋት። ከቅዠቴ ለመንቃት ደቂቃዎች በቂ ነበሩ፡፡ ያገኘችኝ ቦታ ጥላኝ አልሄደችም:: ወደ ቤቷ ወሰደችኝ፡፡ ባሏና የእንጀራ ልጇ መሆናቸውን ከነገረችኝ ወንዶች ጋር የቅብጠት ኑሮ ነበር የምትኖረው። ያላቸው ትስስር ጥብቀት ምን ያህል የተገመደ መሆኑን ባላውቅም አብሯት በሚኖረው የእንጀራ ልጇ ቀናሁ።
ስለእናቴ ልጠይቀው ተመኘሁ። ግን እድሉን አላገኘሁም።በእርግጥ ልጇ መሆኔን ለአንዳቸውም መንገሯን
እጠራጠራለሁ።ልጁ አብሯቸው ቢኖርም ብቸኛ ይመስላል፡፡ቤታቸው ውስጥ ለጊዜው ትኩረት ልሰጠው ያልፈለግኩት የሆነ ልክ ያልሆነ ነገር እንዳለ ተሰምቶኛል፡፡
ምን ልታደርጊ መጣሽ?" ስትለኝ ፊቷ ላይ የነበረው መሸከክ ቢያስደነግጠኝም ምክንያቴን እስክነግራት ነው
ብዬ ራሴን አበረታሁ። የሆንኩትን ሁሉ ከዓይኔ የሚፈሰውን እንባና የአፍንጫዬን ንፍጥ በእጄ አይበሉባ እየሞዠቅኩ ነገርኳት።
"እና? እከክሽን እያከክሽ ከመኖር አይሻልሽም? ወይስ እድሜ ልክሽን በየአውድማው ከጎረምሳ ጋር እየተላፋሽ መኖር ነው የምትፈልጊው? ዝቀሽ የማትጨርሺው ሀብት ላይ ስለጣለሽ
ልታመሰግኚው ሲገባ አባቴን የምትኮንኚው ምን አድርግ ብለሽ
ነው?" ነበር ለለቅሶዬና ለብሶቴ መልሷ። ከዚህ በላይ ልትሰማኝ አንድ ደቂቃ አላባከነችም። በሚቀጥለው ቀን ተመልሼ ባሌ ያደረጉት ተፈሪጋ ለመሄድ እንድስናዳ ነገረችኝ፡፡
"እርሺው እኔ እስከዛሬ እናትሽ እንዳልነበርኩ ሁሉ ከዚህ በኋላም
እናትሽ ልሆን አልችልም።ሰበብ እየፈለግሽ ልታገኚኝ እንዳትሞክሪ።" የሚል ማስጠንቀቂያ አከለችበት። የተሰማኝ ስሜት አልነበረም።ምክንያቱም ደንዝዣለሁ። ከተቀመጥኩበት
ለመነሳት ሰውነቴ እንደወትሮው የሚታጠፍ የሚዘረጋ እስከማይመስለኝ በድኛለሁ። በጠዋት የቀሰቀሰችኝ የትራንስፖርት ገንዘብ ሰጥታኝ ከቤቷ ልታሰናብተኝ ነበር፡፡ለቀናት የማደርገውን ሁሉ የማደርገው አስቤ አልነበረም።
መላው አካሌ ከጭንቅላቴ ጋር እየተማከረ መንቀሳቀሱን እንጃ፡፡ ራሴን ከተፈሪ ጋር ያለኝን ኑሮ እያለማመድኩት አገኘሁት።ብቸኛው ፍቅርን ሊያሳየኝ የሚሞክር ፍጡር እሱ ነው።እውነቱን ነው ግን? እያልኩ አስባለሁ። ስለ ወለደችኝ ሴት ከማሰብ የላቀ የምሰራው የዛሬም ሆነ የነገ እቅድ ስላልነበረኝ እሱ የሚያቅድልኝን ውሎ እውላለሁ። መኪና መንዳት መማር፣የምግብ አሰራር ስልጠና ሙያ መሰልጠን፣ ከጓደኞቹ ሚስቶች
ጋር ተማክሮ ገዝቶ በሚያመጣልኝ ልብስና ጫማ ራሴን ለእርሱ ማስጌጥ፣ ፀጉሬን መሰራት እንዳለብኝ አሳስቦኝ በወጣ ቀን ጠዋት የራስ ቅሌን ለፀጉር ሰሪዎቹ እጅ መስጠት፣ ሊተኛኝ ፈልጎ ሲያላዝን በጀርባዬ ተጋድሜ እግሮቼን መክፈት፣በስራ ሰበብ ሲወሰልት ያደረ ቀን በጠዋት ገዝቶ የሚመጣው በግ መስራት.....(አይነግረኝም።አውቃለሁ።
እንደማውቅ ያውቃል።መፀፀቱን አያቆምም።መወስለቱንም እንደዛው። ከሌላ ሴት ጋር ማደሩን ማወቄ ግድ አይሰጠኝም ነበር፡፡ ምናልባት ለእርሱ ግድ ስለሌለኝ አልያም ለራሴ ግድ
ስለሌለኝ ወይ ደግሞ በሆነች የሀሳቤ ጥግ ሌላ ሴት ለመፈለጉ ምክንያት የራሴ መበደን መቀበሌ ይሆናል የዓመታት ባሌ ከሌላ ሴት ጋር በማደሩ ለሚሰማው ፀፀት ማስተሰሪያ የበግ ደም ማፍሰሱን መቀበሌ።)
በራሷ ጭንቅላት የምታስብ ሴት መሆኔ ጠፍቶ በተፈሪ ባወጣልኝ የእለት መመሪያ የምንቀሳቀስ ሮቦት ለመሆን የፈጀብኝ
ጥቂት ወራት ነው። ተፈሪ በስራው ምክንያት ከከተማ እስካልወጣ ድረስ ቀላል ግልፅ እና ተመሳሳይ የአስራ ስድስት ዓመት ውሎ...
የሚወደውን ምግብ ማብሰል፣ ሱቅ ወጥቶ የሚያስፈልግ ነገር መገዛዛት፣ እሱ እንድሆንለት የሚፈልጋትን ንፁህና ዘናጭ ሴት ሆኜ መጎለት፣ እላዬ ላይ ራቁቱን
እየተወዛወዘ መቼ ልጅ እንደምወልድለት ሲነዛነዝ መስማት፡፡
በራሴ ጭንቅላት የማደርገው ብቸኛ ነገር ለእናቴ ስልክ እየደወልኩ በስልኩ ሞገድ ድንዛዜን ማጨድ ብቻ ነው:: የተለየ
ነገር ከአፏ እንዲወጣ በመናፈቅ ሳልታክት ደውልላታለሁ።ከሚቆጠሩ ቃላት የዘለለ አታናግረኝም። ለምጠይቃት ጥያቄ
መልስ አትመልስልኝም። ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ባሏ ነኝ ያለ ሰውዬ በዚያ ስልክ እንደማላገኛት ነገረኝ፡፡ ደጋግሜ ብደውልም መልሱ ተመሳሳይ ነበር፡፡ የሆነ እለት እንደአበደ ሰው ተነስቼ
ቤቷ ሄድኩ፡፡ ከቤቷ ከወጣች መሰንበቷን ባሏ የነበረው ሰው እየተነጫነጨ ነገረኝ። የት መሆኗን ሊነግረኝ አልፈለገም ከብዙ ወራት በኋላ በተለመደ ውሎዬ መሃከል ያልተለመደ ስልክ ጥሪ አስተናገድኩ፡፡ አባባ ነበረ። ድምፁን ስሰማ እስከዛ ቀን ድረስ ደህንነቴ ወይ ምቾቴ ግድ ሰጥቶት ደውሉልኝ አለማወቁን እረስቼ ናፍቆቴን ገለፅኩለት: የአቧራ ብናኝ ያህል ግድ
አልሰጠውም:: የእናቴ ባል ስለሞተ ለቅሶ እንድደርስ ነገረኝ። ሟች ባሏ ድጋሚ እሷን ለማየት ምክንያት ስለሆነኝ መሞቱ
አስፈነደቀኝ፡፡ ከተፈሪ ጋር ለቅሶ ለመድረስ ሄድን፡፡ ዘመዶቼ ለቅሶውን የነገረኝ አባባን ጨምሮ ማንም ያለመምጣታቸው
አስገረመኝ፡፡ ድንኳኑ ውስጥ ለሟች ባሏ አምርራ ስታለቅስ ሳያት ድፍርስርስ ያለ ስሜት ተሰማኝ፡፡ ለባሏ ስትነፋረቅ ሳያት
ቅናት አነደደኝ፡፡ ለደንዳና ልቧ የሰጠሁት አንዱ ማስተባበያዬ ፉርሽ ሆነብኝ፡፡ ለአፍታ ተፈጥሮዋ ድንጋይነት እንደሆነ ሳምን መሰንበቴ ተሰረዞ ሌላ ነገር የገባኝ መሰለኝ፡፡ ሴትየዋ ከኔ ውጪ
ላለ ሰው ልቧ ስጋ እና ደም ነው ብዬ አሰብኩ፡፡ የሟች ልጅ ነው ያለችኝ ወጣት በአባቱ ሞት ያዘነ አይመስልም። እንደታዛቢ ለቀስተኛውን ይገረምማል:: አመሻሹን የለቅሶ ግርግር ሲበርድ
ጠብቄ ባገኘኋት ስንጣቂ አጋጣሚ ተጠቅሜ እያቀፍኳት ምን ያህል እንዳዘንኩ የልቧ በራፍ ያስጠጋኛል
ብዬ በተለማመድኳቸው ቃላት ነገርኳት። ለደቂቃ በእውነታ የሌለሁ የምቃዥ መሰለኝ፡፡ መልሳ አቅፋኝ አመሰገነችኝ፡፡ ካገባሁት ለመጀመሪያ ጊዜ ከተፈሪ ጋር እንደቅርብ ሰው ስለእርሷ እቅፍ
ንዝረት አብራራሁለት:: ከድንኳኑ ይዤው ወጥቼ ስለእኔ የማያውቀውን ታሪክ በደስታ እየፈነደቅኩ ነገርኩት፡፡ በደሜ
የሚንቀለቀለው እሳት የገባው መሰለኝ:: ባይገባውም ግድ አልነበረኝም። እናቴ ባቀፈችኝ በዛች ደቂቃ ዓለም ቀጥ ብላ
የተፈጥሮ ዑደቶች “ሀ” ብለው አዲስ ቀመር መቀመር እንደጀመሩ ነው የተሰማኝ፡፡ ደስታዬ የተጋባበት መሰለ። ወደ ድንኳኑ ስንመለስ ጨለማው ውስጥ የሳቅ ድምፅ የሰማሁ መሰለኝ፡፡ ምን አስቤ እንደሆነ አላውቅም ተፈሪን በቆመበት ትቼው ወደ ሰማሁት ድምፅ ተራመድኩ፡፡ እናቴ ናት፡፡ ቅድም የነፍስ አባቷ መሆኑን ሲያወሩ ከሰማሁት ሰው ጋር ጨለማው ውስጥ እየተላፉ ይሳሳቃሉ። የነፍስ አባቷ አፉን ድንቅፍ እንኳን አይለው ከሟች በመገላገላቸው የጀመሩትን የድብቅ ፍቅር
👍2
ያለሰቀቀን ሊኮሞክሙ መሆኑን ሲናገር ስሰማው ከዛ በላይ መቆም እንደሌለብኝ ተሰማኝ፡፡ ሴትየዋ ማን ናት? ለሞተው ባሏ
የምታለቅሰው የውሸቷን ነበር?
በሚቀጥለው ቀን ከጠዋት ይልቅ ለለሊት በቀረበ ሰዓት በመኝታ ቤቷ ከተፈሪ ጋር አንድ ላይ ልታናግረን እንደምትፈልግ
መልዕክት የተነገረኝ እስከዛሬ መተኛቴን ከማላስታውሰው ጣፋጭ እንቅልፍ ተቀስቅሼ ነው።
"አቶ ተፈሪ በሃዘኔ ከጎኔ ለመገኘት ስለመጣህ ከልቤ አመሰግናለሁ:: ከዚህ በኋላ ብትቆይ ደስተኛ አልሆንም::
ሚስትህን ይዘህልኝ ወደ ቤትህ ተመለስ፡፡" ይሄን ስትናገር
ከተፈሪ ጎን መቆሜን ሆነ ብላ ረስታዋለች:: ተፈሪ ቃል ከአንደበቱ ለማውጣት የሚያስችል መረዳት አልገባውም። ዓይኑን እያቁለጨለጨ ያያታል፡፡
''በሀዘንሽ ከጎንሽ መሆኔ የቱጋ ነው ሀጢያቱ?" አልኳት:: እንባዬ
ከመጀመሪያው ፊደል እኩል ከዓይኔ እያመለጠ፡፡ ሆን ብላ አልሰማችኝም::
'ቁርስ እንዲያዘጋጁልህ ነግሪያለሁ:: ሰላም ግባ!” ብላ ለሰላምታ
እጇን ዘረጋችለት እኔ እዛ እንደሌለሁ ሁሉ ዓይኗን ከእርሱ ላይ ሳትነቅል:: ለተዘረጋ እጂ አፀፋውን በመመለስ ምትክ እኔን
በህፃን ግራ መጋባት ያየኛል። ዓይኖቿ እኔ ላይ እንዲያርፉ በተዘረጋ እጁና በተፈሪ መሃከል ገብቼ ቆምኩ። እጇን ልትሰበስብ
ስታሸሽ መንጭቄ ያዝኳት፡፡
"በሃዘንሽ ላፅናናሽ መምጣቴ ምንድነው ጥፋቴ? ቆይ ይሄን ያህል ምንድነው ያደረግኩሽ?" አልኳት እጇን ተጭኜ እንደያዝኳት እየታወቀኝ፡፡ ዓይኖቿን ዓይኖቼ ውስጥ በጥልቀት ዘፈቀቻቸው።
"አንድ ነገር ልንገርሽ፡፡ እስከዛሬ ድረስ አንቺ ያመጣሽብኝን ያህል ለመፅናናት የከበደ ሀዘን ገጥሞኝ አያውቅም:: ያኔ መፅናናት ከቻልኩ ዛሬ አፅናኝ አልፈልግም:: ካላየሁሽ እፅናናለሁ::" ብላኝ እንዳደነዘዘችኝ እጇን መንጭቃኝ በቁምኩበት ጥላኝ ወጣች።
የሆነ ነገር ማለት እፈልጋለሁ። ግን አልቻልኩም:: ተፈሪ እጄን ይዞ መኪናችን ድረስ ግራ የገባው ቁጥር አልባ ጥያቄ እኔን ይሁን እሷን ወይም ራሱን እየጠየቀ አደረሰኝ፡፡ ይህ አጋጣሚ የቀየረው ተፈሪን ብቻ ሆነ፡፡ ከእናቴ ጋር ያለኝን ውስብስብ
ሊፈታ መታገል ጀመረ:: በእኔ ፈንታ አዘውትሮ ሊያገኛት ታተረ ከለቅሶ በኋላ የቀድሞ ቤቷን ትታ ማንም ሊነግረን
ወዳላወቀው ቦታ መሄዷን አወቅን፡፡ ተፈሪ ከብዙ መፍጨርጨር በኋላ ተስፋ ቆርጦ ሁሉንም ባለበት ተወው:: ከድንዛዜዬ
የለዘብኩ የመሰለው ቀን ከእናቴ ውጪ መኖር እንደምችል ሊያስረዳኝ ይሞክራል፡፡ ዓለም በብዙ ደግ ልብ ባላቸው መልካም ሰዎች መሞላቷን ይዘበዝብልኛል፡፡
በድጋሚ እናቴን እንዳያት ያስቻለኝ አጋጣሚ የሴት አያቴ ሞት ነበር። አያቴ ከጭካኔና ከመርዛም ቃላት የተሻለ የተወችልኝ ትዝታ ባይኖርም በመሞቷ አዘንኩ፡፡ እናቴ ለያዥ ገናዥ አስቸግራ ስታለቅስ ሳያት አልዋጥልሽ እያለኝ በትዝብት አፈጥባታለሁ፡፡ ላናግራት ስሞክር ትሸሸኛለች:: አልያም
በእናትነቷ ተስፋ ቆርጬ እንድተዋት አንጀት የሚቆርጡ ቃላት ትነግረኛለች::
"አንቺ ማለት ማስታወስ የማልፈልገው ሳስታውሰው ሚጥሚጣ እንደነዙበት ቁስል የሚያቃጥል ንዳድ ያለው ትዝታዬ ነሽ፡፡.....
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
የምታለቅሰው የውሸቷን ነበር?
በሚቀጥለው ቀን ከጠዋት ይልቅ ለለሊት በቀረበ ሰዓት በመኝታ ቤቷ ከተፈሪ ጋር አንድ ላይ ልታናግረን እንደምትፈልግ
መልዕክት የተነገረኝ እስከዛሬ መተኛቴን ከማላስታውሰው ጣፋጭ እንቅልፍ ተቀስቅሼ ነው።
"አቶ ተፈሪ በሃዘኔ ከጎኔ ለመገኘት ስለመጣህ ከልቤ አመሰግናለሁ:: ከዚህ በኋላ ብትቆይ ደስተኛ አልሆንም::
ሚስትህን ይዘህልኝ ወደ ቤትህ ተመለስ፡፡" ይሄን ስትናገር
ከተፈሪ ጎን መቆሜን ሆነ ብላ ረስታዋለች:: ተፈሪ ቃል ከአንደበቱ ለማውጣት የሚያስችል መረዳት አልገባውም። ዓይኑን እያቁለጨለጨ ያያታል፡፡
''በሀዘንሽ ከጎንሽ መሆኔ የቱጋ ነው ሀጢያቱ?" አልኳት:: እንባዬ
ከመጀመሪያው ፊደል እኩል ከዓይኔ እያመለጠ፡፡ ሆን ብላ አልሰማችኝም::
'ቁርስ እንዲያዘጋጁልህ ነግሪያለሁ:: ሰላም ግባ!” ብላ ለሰላምታ
እጇን ዘረጋችለት እኔ እዛ እንደሌለሁ ሁሉ ዓይኗን ከእርሱ ላይ ሳትነቅል:: ለተዘረጋ እጂ አፀፋውን በመመለስ ምትክ እኔን
በህፃን ግራ መጋባት ያየኛል። ዓይኖቿ እኔ ላይ እንዲያርፉ በተዘረጋ እጁና በተፈሪ መሃከል ገብቼ ቆምኩ። እጇን ልትሰበስብ
ስታሸሽ መንጭቄ ያዝኳት፡፡
"በሃዘንሽ ላፅናናሽ መምጣቴ ምንድነው ጥፋቴ? ቆይ ይሄን ያህል ምንድነው ያደረግኩሽ?" አልኳት እጇን ተጭኜ እንደያዝኳት እየታወቀኝ፡፡ ዓይኖቿን ዓይኖቼ ውስጥ በጥልቀት ዘፈቀቻቸው።
"አንድ ነገር ልንገርሽ፡፡ እስከዛሬ ድረስ አንቺ ያመጣሽብኝን ያህል ለመፅናናት የከበደ ሀዘን ገጥሞኝ አያውቅም:: ያኔ መፅናናት ከቻልኩ ዛሬ አፅናኝ አልፈልግም:: ካላየሁሽ እፅናናለሁ::" ብላኝ እንዳደነዘዘችኝ እጇን መንጭቃኝ በቁምኩበት ጥላኝ ወጣች።
የሆነ ነገር ማለት እፈልጋለሁ። ግን አልቻልኩም:: ተፈሪ እጄን ይዞ መኪናችን ድረስ ግራ የገባው ቁጥር አልባ ጥያቄ እኔን ይሁን እሷን ወይም ራሱን እየጠየቀ አደረሰኝ፡፡ ይህ አጋጣሚ የቀየረው ተፈሪን ብቻ ሆነ፡፡ ከእናቴ ጋር ያለኝን ውስብስብ
ሊፈታ መታገል ጀመረ:: በእኔ ፈንታ አዘውትሮ ሊያገኛት ታተረ ከለቅሶ በኋላ የቀድሞ ቤቷን ትታ ማንም ሊነግረን
ወዳላወቀው ቦታ መሄዷን አወቅን፡፡ ተፈሪ ከብዙ መፍጨርጨር በኋላ ተስፋ ቆርጦ ሁሉንም ባለበት ተወው:: ከድንዛዜዬ
የለዘብኩ የመሰለው ቀን ከእናቴ ውጪ መኖር እንደምችል ሊያስረዳኝ ይሞክራል፡፡ ዓለም በብዙ ደግ ልብ ባላቸው መልካም ሰዎች መሞላቷን ይዘበዝብልኛል፡፡
በድጋሚ እናቴን እንዳያት ያስቻለኝ አጋጣሚ የሴት አያቴ ሞት ነበር። አያቴ ከጭካኔና ከመርዛም ቃላት የተሻለ የተወችልኝ ትዝታ ባይኖርም በመሞቷ አዘንኩ፡፡ እናቴ ለያዥ ገናዥ አስቸግራ ስታለቅስ ሳያት አልዋጥልሽ እያለኝ በትዝብት አፈጥባታለሁ፡፡ ላናግራት ስሞክር ትሸሸኛለች:: አልያም
በእናትነቷ ተስፋ ቆርጬ እንድተዋት አንጀት የሚቆርጡ ቃላት ትነግረኛለች::
"አንቺ ማለት ማስታወስ የማልፈልገው ሳስታውሰው ሚጥሚጣ እንደነዙበት ቁስል የሚያቃጥል ንዳድ ያለው ትዝታዬ ነሽ፡፡.....
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍1
#የማለዳ_ራእይ!
ናፍቆትሽ ፀናብኝ
ብየ ስልክልሽ
‘አይዞህ ' አይባልም
መከሰት ነው እንጂ በገሀድ ወይ በህልም !
ካጨሽ አሰናብቺ
ትዳር ካለሽ ፍቺ
ለኔ ለምመኝሽ ሁሉን ነገር ስጪ
የህሊና ቀጪ
የልቦና ስሜት
ይሉንታና ሀሜት
ያገር ሰው ሽሙጥም
ከምኞቴ አይበልጥም ::
ተሊቀመላኩ
ክንፍ ተበድረሽ
ነፋስ ቀድመሽ በረሽ
ባለሁበት አገር
እንደ ሸዋዚንገር
ብረት ለበስ ጡንቻ
ባንድ ርግጫ ብቻ
የቤቴን በር ሰብረሽ
ዐይነ ርግብሽ ወድያ
ቀሚስሽ ወደ ላይ
ወደኔ በጥድፍያ
ወዳልጋው በዝላይ
በጀርባየ ሁኘ
ከእግሮቼ መካከል የጠላ ምልክት
አንቺ ጆሮ ሆነሽ
እኔ ሎቲ ሆኘ-ተጣጥሞ ስክት !
እንዲህ እያሰበ ገላየ ሲቸገር
መጣሁ ትያለሽ ስል
“አይዞህ “ ብሎ ነገር፤
የማለዳ ራእይ፤ ምኞቴን በማመን
በገሀድም ይሁን፤ ወይም በሰመመን
አሳትፊኝ አልሁ እንጂ
ከገላሽ በረከት፤ ከሙቀት ከለዛው
የቃል ምፅዋትማ ሞልቷል በየታዛው!
🔘በእውቀቱ ስዩም🔘
ናፍቆትሽ ፀናብኝ
ብየ ስልክልሽ
‘አይዞህ ' አይባልም
መከሰት ነው እንጂ በገሀድ ወይ በህልም !
ካጨሽ አሰናብቺ
ትዳር ካለሽ ፍቺ
ለኔ ለምመኝሽ ሁሉን ነገር ስጪ
የህሊና ቀጪ
የልቦና ስሜት
ይሉንታና ሀሜት
ያገር ሰው ሽሙጥም
ከምኞቴ አይበልጥም ::
ተሊቀመላኩ
ክንፍ ተበድረሽ
ነፋስ ቀድመሽ በረሽ
ባለሁበት አገር
እንደ ሸዋዚንገር
ብረት ለበስ ጡንቻ
ባንድ ርግጫ ብቻ
የቤቴን በር ሰብረሽ
ዐይነ ርግብሽ ወድያ
ቀሚስሽ ወደ ላይ
ወደኔ በጥድፍያ
ወዳልጋው በዝላይ
በጀርባየ ሁኘ
ከእግሮቼ መካከል የጠላ ምልክት
አንቺ ጆሮ ሆነሽ
እኔ ሎቲ ሆኘ-ተጣጥሞ ስክት !
እንዲህ እያሰበ ገላየ ሲቸገር
መጣሁ ትያለሽ ስል
“አይዞህ “ ብሎ ነገር፤
የማለዳ ራእይ፤ ምኞቴን በማመን
በገሀድም ይሁን፤ ወይም በሰመመን
አሳትፊኝ አልሁ እንጂ
ከገላሽ በረከት፤ ከሙቀት ከለዛው
የቃል ምፅዋትማ ሞልቷል በየታዛው!
🔘በእውቀቱ ስዩም🔘
#ቀላውጦ_ማስመለስ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
እባክሽ ተይኝ! ሳይሽ የሚሰማኝ እንደዛ ነው። እርሺኝ፡፡" አለችኝ የእናቷን ለቅሶ አብቅታ ልትመለስ የተነሳች እለት። የምትናገረኝ ሁሉ ለምን ተስፋ እንደማያስቆርጠኝ አይገባኝም።
ከዓመታት በኋላ ስለእርሷ በማሰብ መታተሬን ለማቆም በምታገልበት ወቅት ነው ታማ መተኛቷንና ልታየኝ መፈለጓን
በመልዕክተኛ የላከችብኝ፡፡
አመሻሽ ላይ ታክሲ ተሳፍሬ ሆስፒታሉ ደጅ የሄድኩት የመኪና ማቆሚያው ጋር የተውኩትን መኪና ለመውሰድ ነበር፡፡ ራሴን ያገኘሁት እናቴ የተኛችበት ክፍል ውስጥ ነው።ማንም የለም። ተመልሼ ዓይኗን የማየት ምንም ሀሳብ በጭንቅላቴ አልነበረም፡፡እዛ ስላየችኝ እንዳልተገረመች ሁሉ የተለየ ገፅታ አላሳየችኝም።
ከለመድኩት በተለየ ዓረፍተ ነገር አልነበረም አፏን ያላቀቀችው።
"ደሞ ምን ቀርቶሽ መጣሽ?"
አልመለስኩላትም። እዚህኛው የስሜት ወለል ላይ ቆሜ ለሷ ያለኝ ስሜት ፍቅር ይሁን ጥላቻ ተዳቅሎብኛል፡፡ ምናልባት
እሷን እየወደድኳት በመሰለኝ ጊዜ ሁሉ ራሴን አጥብቄ እየወደድኩ ይሆናል፡፡ በሷ ፍቅር የእኔን የመኖር መሰረት ላመጣል ይሆናል ፍቅሯን የሙጥኝ ያልኩት:: መራርነቷ ቀደምስሬ ትኩስ ደም ሆኖ ሲያግለኝ አካሌ የተወጣጠረ አይነት
ስሜት ተሰማኝ፡፡ ተራራ የሚያክል ምክንያት ቢኖራት እንኳን በዕድሜ ቁጥሯ የሰናፍጭ ታክል ቅንጣት መራር አስተዋፅኦ
ያላበረከትኩ እኔን ለመጥላት እና ቀኖቼን በጥላቻ ለማመሳቀል በቂ እንደማይሆን እያሰብኩ የሆስፒታሉ አልጋ ላይ ተኝታ ሳያት
"ከእሷ ሰንሰለት ራሴን ነፃ ማውጣት አለብኝ፡፡" አልኩት ራሴን::
ያሰብኩትን ባሰብኩ ቅፅበት እጅና እግሬ ለመተግበር ተዘርግተዋል፡፡ የማደርገውን ነገር ውጤት ለማሰላሰል የተረፈ
ስንዝር ክፍተት ጭንቅላቴ ውስጥ አልተረፈም።ጭንቅላቴ በብስጭት በፈላ ደም ብቻ የተሞላ ይመስለኛል፡፡
ያደረግኩት ነገር ሀጢያት ይሁን ፅድቅ ግድ አልነበረኝም።ፅድቅና ሀጢያትን ከህሊናዬ ውጪ የት ተማርኩት? ህሊናዬ
የቸረኝ ትልቁ ስጦታዬስ_ዘብራቃ ቀኖችን ብቻ አይደል?ላደረግኩት ድርጊት ስም መለጠፍ አላሻኝም:: ብቻ ግን
የሆስፒታሉን ቅጥር ጊቢ ለቅቄ ስወጣ መቼ እንደሳቅኩ የማላስታውሰውን ድምፅ ያለው ሳቅ ሳቅኩ: በመኪናዬ መስኮት
እየገባ ጉንጨን እየዳበሰ እና ፀጉሬን እየገለበ ከሚያባብለኝ ንፋስ
ጋር እየተጫወትኩ እቤት ስደርስ ተፈሪ ሳሎን ተቀምጦ በቴሌቭዥን ተከታታይ የአማርኛ ድራማ እያየ ነበር።
በደመነፍስ ወይም ለእርሱ ብዬ ያደረግኩት ነገር አልነበረም።ልብሴን አወላልቄ ስጨርስ የእርሱን የሚቀጥል እርምጃ አልጠበቅኩም:: ያለማቋረጥ እየፈገግኩ መሆኔ ይታወቀኛል።
በሁኔታዬ ግራ መጋባቱን ሳይደብቅ የራሱን ልብሶች በመግፈፍ አገዘኝ፡፡ ግራ ቢጋባም ልብሴ ወልቆ ካየኝ ምክንያትና ድርጊት ለማሰብ የሚተርፍ ጭንቅላት እንደማይኖረው አውቃለሁ።በራሴው የውዝዋዜ ስልት አብረን ጮቤ ረገጥን፡፡ ሳቃስት ራሴን መስማቴ መልሶ አስፈገገኝ።
"መቼ ነው ልጅ የምንወልደው? ልጆች እንዲኖሩን እፈልጋለሁ::" የተለመደ ውትወታውን ከወንድ ርጭቱ እና
ከረዥሙ ትንፋሹ ጋር ደምሮ ጠየቀኝ።
በፍፁም እናት መሆን አልፈልግም በፍፁም ልጅ አይኖረኝም።" ለመጀመሪያ ጊዜ መለስኩለት ፈ።
ለምን? ለምን? ከኔ መውለድ ነው የማትፈልጊው ?"
"አይደለም።እናት ምን እንደሆነች አላውቅም እናት መሆን የምችል አይመስለኝም:: እናት የማልሆነውን ልጅ ወደዝህች ምድር ማምጣት አልፈልግም::" መልሴ አጥጋቢ ሆኖለት ይሁን ደስታውን ላለመበረዝ ርዕሱን መቀየር ፈለገ፡፡
"የዛሬው ነገር ማለቴ የማላውቃት ሴት የሆንሽበት ሚስጥር ምንድነው?" ሲለኝና የበር መጥሪያው ሲጮህ አንድ ሆነ፡፡
“ነፃነቴን አገኘሁ::" አልኩት ልብሶቼን እየለባበስኩ፡፡የሚቀጥለውን ጥያቄ ከአፉ ላይ አስቀርቶት ልብሱን እንደነገሩ
ደራርቦ በር ሊከፍት ወጣ፡፡
"ወይዘሮ ማህሌት አጥጋቢ በወይዘሮ ወለላ አጥጋቢ ነፍስ ማጥፋት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለዋል::" አለ ተፈሪን አጅበውት ወደ ቤት ከዘለቁት ሶስት ፖሊሶች አንደኛው ወደ ፊት ጠጋ ብሎ፡፡
ስህተት መሆን አለበት። በጭራሽ እሷ ሰው አትገድልም:: ከኔ ጋር ነበረች። ስህተት ነው::" ይላል ተፈሪ ተራ በተራ ፖሊሶቹን እያየ:: ወደእኔ ዞሮ ማረጋገጫ ይጠብቃል።
ስህተት አይደለም:: ገድያታለሁ:: እራሴ ነኝ የገደልኳት፡፡ አንቄ ነው የገደልኳት:: ለፖሊስ ደውዬ ያሳወቅኩትም ራሴ ነኝ!"
ካደረግኩት በላይ ፀፀት እንደሌለብኝ እንዲታወቅልኝ የተናገርኩት ነበር፡፡ በመጠኑም እንደ አብሪ ትል ብልጭ እያለ
የጭንቅላቴ ክፍል ከፀፀት ነፃ የተናገርኩት ይመስለኛል።
እጆቼ በብረት ካቴና ተቆልፈው ወደ እስር ቤት እየተወሰድኩ እየተሰማኝ ያለው ወደ ነፃነት ዓለም እየሄድኩ እንደሆነ ነው።
የሰው ልጅ ዓለሙ ያለው ጭንቅላቱ ውስጥ መሆኑ የገባኝ በጭንቅላቴ ማሰብ ስጀምር ነው።ወደ ሚታየው ዓለም ተርጉሞ የሚኖረው በጭንቅላቱ የሰራውን ዓለም መሆን አለበት።ጭንቅላቴ ውስጥ አዲስ የተገነባው ዓለም ነፃነት ያለበት እና
ጥያቄ አልባ ሲሆን የእስር ቤቱ መሬት ከተፈሪ ሶፋ በላይ እንደተመቸኝ አይነት እና በዙሪያዬ የማየው ሁሉ ድሎት ሳለ
በውስጤ ያረጀው ዓለም ጥቀርሻነት ሳቅ ከፊቴ እንዳሸሽብኝ አይነት:: በእርግጥ በሚዳስሰው ዙሪያችን የራሳችንን ዓለም
መገንባት ረዥም ዕድሜን እንደሚፈጅ ሁሉ በጭንቅላታችን ውስጥም ጥቃቅን መሰረቶችን መጣል ሳይቀር የረዥም ጊዜ
ድልዳል ነው:: ገዳይ መሆንም ጭምር!!!! ዳኛው የእስር ዓመቴ ሀያ ዓመት መሆኑን በሞዶሻቸው ጠረጴዛውን በኩርኩም
ነርተው ሲያውጁ በነፃ ያሰናበቱት ወንጀለኛ ገፅታ ነበር ፊቴ ያጋለጠው።የምጓጓለት ቀሪ ኑሮ የለኝምና ነው:: የታሰርኩ ሰሞን ተፈሪ በየእለቱ ይጠይቀኝ ነበር። ሁሉም ሰላም እንደሆነ እና ከወህኒው ጊቢ ማዶ የሚያጓጓኝ የኔ ዓለም እንደሌለ አምኜ እንደደረስ ጎረምሳ በፉጨት ቀኖቼን እየተለማመድኩ ሳለ
ከዓመታት በፊት ያየሁት የእናቴ የእንጀራ ልጅ ከሌላ አንድ ወንድ ጋር እና ሁለት ሴቶች ጋር ሊጎበኘኝ መምጣቱ ከመገረም
በላይ የማይታመን ነገር ሆነብኝ፡ አጠገባቸው ደርሼ ከመቆሜ ከሴቶቹ ጋር ተደጋግፈው በቆሙት አቋቋም ጥንድ ጥንድ መሆናቸው ገባኝ፡፡ ያልገባኝ ምን ሊሰሩ እንደመጡ ነው፡፡....
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
እባክሽ ተይኝ! ሳይሽ የሚሰማኝ እንደዛ ነው። እርሺኝ፡፡" አለችኝ የእናቷን ለቅሶ አብቅታ ልትመለስ የተነሳች እለት። የምትናገረኝ ሁሉ ለምን ተስፋ እንደማያስቆርጠኝ አይገባኝም።
ከዓመታት በኋላ ስለእርሷ በማሰብ መታተሬን ለማቆም በምታገልበት ወቅት ነው ታማ መተኛቷንና ልታየኝ መፈለጓን
በመልዕክተኛ የላከችብኝ፡፡
አመሻሽ ላይ ታክሲ ተሳፍሬ ሆስፒታሉ ደጅ የሄድኩት የመኪና ማቆሚያው ጋር የተውኩትን መኪና ለመውሰድ ነበር፡፡ ራሴን ያገኘሁት እናቴ የተኛችበት ክፍል ውስጥ ነው።ማንም የለም። ተመልሼ ዓይኗን የማየት ምንም ሀሳብ በጭንቅላቴ አልነበረም፡፡እዛ ስላየችኝ እንዳልተገረመች ሁሉ የተለየ ገፅታ አላሳየችኝም።
ከለመድኩት በተለየ ዓረፍተ ነገር አልነበረም አፏን ያላቀቀችው።
"ደሞ ምን ቀርቶሽ መጣሽ?"
አልመለስኩላትም። እዚህኛው የስሜት ወለል ላይ ቆሜ ለሷ ያለኝ ስሜት ፍቅር ይሁን ጥላቻ ተዳቅሎብኛል፡፡ ምናልባት
እሷን እየወደድኳት በመሰለኝ ጊዜ ሁሉ ራሴን አጥብቄ እየወደድኩ ይሆናል፡፡ በሷ ፍቅር የእኔን የመኖር መሰረት ላመጣል ይሆናል ፍቅሯን የሙጥኝ ያልኩት:: መራርነቷ ቀደምስሬ ትኩስ ደም ሆኖ ሲያግለኝ አካሌ የተወጣጠረ አይነት
ስሜት ተሰማኝ፡፡ ተራራ የሚያክል ምክንያት ቢኖራት እንኳን በዕድሜ ቁጥሯ የሰናፍጭ ታክል ቅንጣት መራር አስተዋፅኦ
ያላበረከትኩ እኔን ለመጥላት እና ቀኖቼን በጥላቻ ለማመሳቀል በቂ እንደማይሆን እያሰብኩ የሆስፒታሉ አልጋ ላይ ተኝታ ሳያት
"ከእሷ ሰንሰለት ራሴን ነፃ ማውጣት አለብኝ፡፡" አልኩት ራሴን::
ያሰብኩትን ባሰብኩ ቅፅበት እጅና እግሬ ለመተግበር ተዘርግተዋል፡፡ የማደርገውን ነገር ውጤት ለማሰላሰል የተረፈ
ስንዝር ክፍተት ጭንቅላቴ ውስጥ አልተረፈም።ጭንቅላቴ በብስጭት በፈላ ደም ብቻ የተሞላ ይመስለኛል፡፡
ያደረግኩት ነገር ሀጢያት ይሁን ፅድቅ ግድ አልነበረኝም።ፅድቅና ሀጢያትን ከህሊናዬ ውጪ የት ተማርኩት? ህሊናዬ
የቸረኝ ትልቁ ስጦታዬስ_ዘብራቃ ቀኖችን ብቻ አይደል?ላደረግኩት ድርጊት ስም መለጠፍ አላሻኝም:: ብቻ ግን
የሆስፒታሉን ቅጥር ጊቢ ለቅቄ ስወጣ መቼ እንደሳቅኩ የማላስታውሰውን ድምፅ ያለው ሳቅ ሳቅኩ: በመኪናዬ መስኮት
እየገባ ጉንጨን እየዳበሰ እና ፀጉሬን እየገለበ ከሚያባብለኝ ንፋስ
ጋር እየተጫወትኩ እቤት ስደርስ ተፈሪ ሳሎን ተቀምጦ በቴሌቭዥን ተከታታይ የአማርኛ ድራማ እያየ ነበር።
በደመነፍስ ወይም ለእርሱ ብዬ ያደረግኩት ነገር አልነበረም።ልብሴን አወላልቄ ስጨርስ የእርሱን የሚቀጥል እርምጃ አልጠበቅኩም:: ያለማቋረጥ እየፈገግኩ መሆኔ ይታወቀኛል።
በሁኔታዬ ግራ መጋባቱን ሳይደብቅ የራሱን ልብሶች በመግፈፍ አገዘኝ፡፡ ግራ ቢጋባም ልብሴ ወልቆ ካየኝ ምክንያትና ድርጊት ለማሰብ የሚተርፍ ጭንቅላት እንደማይኖረው አውቃለሁ።በራሴው የውዝዋዜ ስልት አብረን ጮቤ ረገጥን፡፡ ሳቃስት ራሴን መስማቴ መልሶ አስፈገገኝ።
"መቼ ነው ልጅ የምንወልደው? ልጆች እንዲኖሩን እፈልጋለሁ::" የተለመደ ውትወታውን ከወንድ ርጭቱ እና
ከረዥሙ ትንፋሹ ጋር ደምሮ ጠየቀኝ።
በፍፁም እናት መሆን አልፈልግም በፍፁም ልጅ አይኖረኝም።" ለመጀመሪያ ጊዜ መለስኩለት ፈ።
ለምን? ለምን? ከኔ መውለድ ነው የማትፈልጊው ?"
"አይደለም።እናት ምን እንደሆነች አላውቅም እናት መሆን የምችል አይመስለኝም:: እናት የማልሆነውን ልጅ ወደዝህች ምድር ማምጣት አልፈልግም::" መልሴ አጥጋቢ ሆኖለት ይሁን ደስታውን ላለመበረዝ ርዕሱን መቀየር ፈለገ፡፡
"የዛሬው ነገር ማለቴ የማላውቃት ሴት የሆንሽበት ሚስጥር ምንድነው?" ሲለኝና የበር መጥሪያው ሲጮህ አንድ ሆነ፡፡
“ነፃነቴን አገኘሁ::" አልኩት ልብሶቼን እየለባበስኩ፡፡የሚቀጥለውን ጥያቄ ከአፉ ላይ አስቀርቶት ልብሱን እንደነገሩ
ደራርቦ በር ሊከፍት ወጣ፡፡
"ወይዘሮ ማህሌት አጥጋቢ በወይዘሮ ወለላ አጥጋቢ ነፍስ ማጥፋት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለዋል::" አለ ተፈሪን አጅበውት ወደ ቤት ከዘለቁት ሶስት ፖሊሶች አንደኛው ወደ ፊት ጠጋ ብሎ፡፡
ስህተት መሆን አለበት። በጭራሽ እሷ ሰው አትገድልም:: ከኔ ጋር ነበረች። ስህተት ነው::" ይላል ተፈሪ ተራ በተራ ፖሊሶቹን እያየ:: ወደእኔ ዞሮ ማረጋገጫ ይጠብቃል።
ስህተት አይደለም:: ገድያታለሁ:: እራሴ ነኝ የገደልኳት፡፡ አንቄ ነው የገደልኳት:: ለፖሊስ ደውዬ ያሳወቅኩትም ራሴ ነኝ!"
ካደረግኩት በላይ ፀፀት እንደሌለብኝ እንዲታወቅልኝ የተናገርኩት ነበር፡፡ በመጠኑም እንደ አብሪ ትል ብልጭ እያለ
የጭንቅላቴ ክፍል ከፀፀት ነፃ የተናገርኩት ይመስለኛል።
እጆቼ በብረት ካቴና ተቆልፈው ወደ እስር ቤት እየተወሰድኩ እየተሰማኝ ያለው ወደ ነፃነት ዓለም እየሄድኩ እንደሆነ ነው።
የሰው ልጅ ዓለሙ ያለው ጭንቅላቱ ውስጥ መሆኑ የገባኝ በጭንቅላቴ ማሰብ ስጀምር ነው።ወደ ሚታየው ዓለም ተርጉሞ የሚኖረው በጭንቅላቱ የሰራውን ዓለም መሆን አለበት።ጭንቅላቴ ውስጥ አዲስ የተገነባው ዓለም ነፃነት ያለበት እና
ጥያቄ አልባ ሲሆን የእስር ቤቱ መሬት ከተፈሪ ሶፋ በላይ እንደተመቸኝ አይነት እና በዙሪያዬ የማየው ሁሉ ድሎት ሳለ
በውስጤ ያረጀው ዓለም ጥቀርሻነት ሳቅ ከፊቴ እንዳሸሽብኝ አይነት:: በእርግጥ በሚዳስሰው ዙሪያችን የራሳችንን ዓለም
መገንባት ረዥም ዕድሜን እንደሚፈጅ ሁሉ በጭንቅላታችን ውስጥም ጥቃቅን መሰረቶችን መጣል ሳይቀር የረዥም ጊዜ
ድልዳል ነው:: ገዳይ መሆንም ጭምር!!!! ዳኛው የእስር ዓመቴ ሀያ ዓመት መሆኑን በሞዶሻቸው ጠረጴዛውን በኩርኩም
ነርተው ሲያውጁ በነፃ ያሰናበቱት ወንጀለኛ ገፅታ ነበር ፊቴ ያጋለጠው።የምጓጓለት ቀሪ ኑሮ የለኝምና ነው:: የታሰርኩ ሰሞን ተፈሪ በየእለቱ ይጠይቀኝ ነበር። ሁሉም ሰላም እንደሆነ እና ከወህኒው ጊቢ ማዶ የሚያጓጓኝ የኔ ዓለም እንደሌለ አምኜ እንደደረስ ጎረምሳ በፉጨት ቀኖቼን እየተለማመድኩ ሳለ
ከዓመታት በፊት ያየሁት የእናቴ የእንጀራ ልጅ ከሌላ አንድ ወንድ ጋር እና ሁለት ሴቶች ጋር ሊጎበኘኝ መምጣቱ ከመገረም
በላይ የማይታመን ነገር ሆነብኝ፡ አጠገባቸው ደርሼ ከመቆሜ ከሴቶቹ ጋር ተደጋግፈው በቆሙት አቋቋም ጥንድ ጥንድ መሆናቸው ገባኝ፡፡ ያልገባኝ ምን ሊሰሩ እንደመጡ ነው፡፡....
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍4
#የባይተዋር_ገድል
በቁም መስተዋት ፊት መቆምኸ ሲጨንቅህ
የቁም መስታወቱ፣"ሰውነትህ የታል?" ብሎ ሲጠይቅህ
ግድግዳው ላይ ያለች፣የገደል ማሚቱ ዝም ማለት ፈርታ
ሳሎንህን ስትሞላው ዝምህን አብዝታ
ሕልም የቀላቀለ፣የዝናብ ነጠብጣብ፣ ጣራህን ሲመታ
ከመስኮትኸ ማዶ፣የለሊት ወፍ ሞታ
የጊዜ ስውር ክንድ
የጓሮህን ዋርካ ያላገር ሲያስቀረው
በለሊት ወፍ ምትክ፣ክንፍ ያወጣ ሌሊት ጎጆህን ሲዞረው
መርሳት የሚሉት፣የኑሮ ገባር ወንዝ፣ አልጋህን ሲገምሰው
"መንሳፈፍስ ይቅር፣ መስጠም ያቅተዋል ሰው?"
ሲያሰኝህ እድልህ
ያኔ ይጀምራል የባይተዋር ገድልህ
🔘በውቀቱ ስዩም🔘
በቁም መስተዋት ፊት መቆምኸ ሲጨንቅህ
የቁም መስታወቱ፣"ሰውነትህ የታል?" ብሎ ሲጠይቅህ
ግድግዳው ላይ ያለች፣የገደል ማሚቱ ዝም ማለት ፈርታ
ሳሎንህን ስትሞላው ዝምህን አብዝታ
ሕልም የቀላቀለ፣የዝናብ ነጠብጣብ፣ ጣራህን ሲመታ
ከመስኮትኸ ማዶ፣የለሊት ወፍ ሞታ
የጊዜ ስውር ክንድ
የጓሮህን ዋርካ ያላገር ሲያስቀረው
በለሊት ወፍ ምትክ፣ክንፍ ያወጣ ሌሊት ጎጆህን ሲዞረው
መርሳት የሚሉት፣የኑሮ ገባር ወንዝ፣ አልጋህን ሲገምሰው
"መንሳፈፍስ ይቅር፣ መስጠም ያቅተዋል ሰው?"
ሲያሰኝህ እድልህ
ያኔ ይጀምራል የባይተዋር ገድልህ
🔘በውቀቱ ስዩም🔘
#ባለ_አንካሳ_ልብ_ሯጭ
ቅልጥም ለማደደን ቅቤ ከምጠጡ
ጋሬጣን ለማምለጥ ጫማ ከምትመርጡ
የልብ ወጌሻ አምጡ፣
አንካሳ ልብ ያለው ምን በእግሩ ቢሮጥም
ቢያባርር አይዝም ቢሸሽ አያመልጥም።
ቅልጥም ለማደደን ቅቤ ከምጠጡ
ጋሬጣን ለማምለጥ ጫማ ከምትመርጡ
የልብ ወጌሻ አምጡ፣
አንካሳ ልብ ያለው ምን በእግሩ ቢሮጥም
ቢያባርር አይዝም ቢሸሽ አያመልጥም።
#ቀላውጦ_ማስመለስ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት (የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
...ሰላም?” አልኩኝ የማውቀው ፊት ላይ አፍጥጬ።ብዙም ደቂቃ አላባከኑም ወንዶቹ ወንድሞቼ መሆናቸውንና ሴቶቹ
ፍቅረኞቻቸው መሆናቸውን ሲነግሩኝ አልጋ ላይ ሆኜ እየቃዠሁ አለመሆኔን ደጋግሜ ራሴን ስጠይቀው:: ለምን ነበር ወንድሜ መሆኑን እንዳውቅ ያልፈለገችው? ይህቺ ሴትዮ በስንቱ ነው
የምትበድለኝ? ስትሞት ጥያቄዬ ሁሉ አብሯት የሞተና ከዚያ በኋላ መቼም የማያስጨንቀኝ መስሎኝ ነበር፡፡ ነገር
ግን በተቃራኒው ሆነ፡፡ ሞታም ይኸው ግራ እያጋባች ታቀውሰኛለች።
ከተለያየ ወንዶች የወለደቻቸው ሁለት
ወንድሞች አሉኝ፡፡ ምናልባት ሌሎችም ይኖሩ ይሆናል፡፡ምክንያቱም እነርሱም እህት እንዳላቸው ያወቁት ስለገደልኳት
ነው። ሴትየዋ ማን ነበረች? ምንስ ነበር ትርፏ?
ብዙ ዓረፍተ ነገሮች ሳያባክኑ የተረዳሁት ለእነርሱም ጥሩ እናት እንዳልነበረች ነው። ከፍቅራቸው ገዝፎ ጥላቻና መከፋታቸው
ይታያል። ክልሱ ወንድሜ (ኪሩቤል) በተሻለ ፍቅር ነበረው። ስለገደልኳትም ማዘኑን አልደበቀኝም። ታላቃቸው ነኝ
ኪሩቤልን በሶስት ዓመት እበልጠዋለሁ። ቅዱስን በአስራ አንድ ዓመት።
እየተቅለበለበች የምታወራው የቅዱስ ፍቅረኛ በምሰማው ነገር እየተሰማኝ የነበረውን ስሜት ውል መያዝ
እንዳልችል ታስፎርሸኛለች፡፡ የራሷንም የእርሱንም ደምራ በሚቅበጠበጠው መላ አካሏ እየታጀበች የምታወራው እርሷ
ናት። አንዲትም ቃል ሳልተነፍስ የመጠየቂያ ሰዓቱ አልቆ ከመግባቴ በፊት ኪሩቤል እግሩ ስር አስቀምጦት የነበረውን ካርቶን እየሰጠኝ ይሄ አንቺ ትፅፊላት የነበሩት ደብዳቤዎች ናቸው። ከአጠገቧ ተለይቷት አያውቅም። ሆስፒታል እንኳን አብረዋት ነበሩ።
ያንቺ መሆኑን ያወቅነው ከሞተች በኋላ
ነው። ለነዚህ ደብዳቤዎች ፍቅር እንደነበራት አውቃለሁ። እያነበበች
ትንሰቀሰቅ ነበር። ምናልባት የምትፈልጊው ከሆነ ብለን ነው።"
አለኝ፡፡ የነገረኝ ነገር እኔ ውስጥ የሚፈጥረውን ውስብስብ ሳይረዳ፡፡
"ከእኔ ከልጇ በላይ አንቺ የምትፅፊላት ደብዳቤ ትርጉም ነበረው።ማን መሆንሽን ሳላውቅ ብዙ ጊዜ ቀንቼብሻለሁ::" አለ እስካሁን ከንግግር የተቆጠበው ቅዱስ፡፡ በስልክ ላገኛት ባለመቻሌ እቤቷ የሄድኩ ጊዜ ባሏ ነበረ የፖስታ አድራሻዋን የስጠኝ፡፡ ታንብበው አታንብበው እንኳን ሳላውቅ በየወሩ እፅፍላት ነበር፡፡ አንዳንዴ
ባታነበው እንኳን የውስጤን እየተነፈስኩ ስለሚመስለኝ መፃፌን አላቆምም ነበር። ስለእርሷ ለመርሳት መሞከር በጀመርኩ ጊዜ ከጥቂት ዓመታት በፊት ነው መፃፌን ያቋረጥኩት፡፡ተሰናብተውኝ ከሄዱ በኋላ ምን ማሰብና የቱን ማመን እንዳለብኝ
ግራ ተጋባሁ። ትወደኝ ነበር? ትጠላኝ ነበር? ትፀፀት ነበር? የትኛው ነበር ልኩ? የምታሳየኝ ጥላቻ ወይስ የደበቀችኝ ፀፀት?ለቀናት በጥቅጥቅ የጥያቄ ጫካ ውስጥ ተቅበዘበዝኩ። ጠፋሁ። መውጫው የማይገኝ ሆኖብኝ ባተትኩ። ማን ነበረች ይህቺ ሴትዮ?
ኪሩቤል አዘውትሮ መምጣቱን በቀጠለ መጠን ስለእርሷ የሚነግረኝ ነገር ሌላ የማላውቀው የእርሷ ገፅታ ነው።ሁሌም
በመጣ ቁጥር በሞቷ እናቱን እንዳሳጣሁት ይወቅሰኝ ስለነበር
በአንዱ ቀን የበደሌን ግዝፈት ልከምርለት አፌን ለማላቀቅ ተገደድኩ፡፡ የረጋ ቀልብ ያላት ፍቅረኛው በእንባዬ ጠብታ ልክ
እንባዋን እያፈሰሰች ስትሰማኝ እርሱ በጭንቀት ሲንቆራጠጥ ቆይቶ ምንም ቃል ሳይተነፍስ ሄደ፡፡ ለወቀሳው የመጨረሻ ቀን ሆነ፡፡ በፍቅረኛው ተገዶ የሚመጣ የሚመስለኝ ቅዱስ አልፎ
አልፎ ቢመጣም እርሷ ታወራለታለች እንጂ በዝምታ ሰዓቱን ጨረሶ ነበር የሚሰናበተኝ። በቃላት ባይናገረውም አምርሮ እንደሚጠላት መደበቅ አይችልም።የሁሉም ዑደት አንድ ጫፍ ላይ ገተረኝ ማናችንም ሴትየዋን አናውቃትም ልናውቃትም አንችልም። እንቆቅልሽ ነበረች:ፈ።ከነእንቆቅልሿ ተቀብራለች።ይሄን እያሰብኩ የእስር ቤት ቀኖቼን ልረሳት እራሴን እመክራለሁ፡፡ ወንድሞቼ እና ፍቅረኞቻቸው ሲመጡ ወጥቼ ሳገኛቸው ስለእነርሱ የሚሰማኝን ስሜት እፈትሻለሁ። በየእለቱ ተፈሪ ሊጎበኘኝ ሲመጣ አግብቶ እንዲወልድ እነግረዋለሁ።የታሰርኩ ሰሞን በየእለቱ፣ ጊዜው ሲገፋፋ በሁለት ቀን፣ ሲዘገይ
በሳምንት፣ ከራርሞ በወር፣ ሰነባብቶ ጭራሹኑ ቀረ።
ከእያንዳንዱ ክፋት ጀርባ መሪር በደል አለ እያልኩ አስባለሁ።ጥያቄው የሚሆነው በደልን ይቅር ያለ በጎነት የለም ወይ?
የሚለው ነው። ኖሮ ያውቅ ይሆናል፡ በደልን ይቅር ለማለት የሚያስችል ትልቅ በጎነት የሚፈጥር ፍቅር የሚጠይቅ
ይመስለኛል። የገባኝ በዛ መጠን በልቤ የተንሰራፋ መልካምነት መፍጠር የሚችል ከተበደልኩት ልቆ የሚገዝፍ ፍቅር የለኝም። እናቴን ልገድልበት የቻልኩበትን ቅፅበት ሳስብ በሰውኛ ምክንያት
ከመግመድ አይሎ ቅፅበታዊ ስሜት መላው አካላችንን የሚያዝበት አጋጣሚ መኖሩን ነው። ከታሰርኩ ከብዙ ወራት
በኋላ ጠየቂ እንደመጣልኝ ፖሊሷ ነገረችኝ፡፡ ከወንድሞቼ አንዳቸው እንደሚሆኑ እያሰብኩ ስወጣ ፖሊሷ የጠቆመችኝ ያለዛሬ አይቼ የማላውቀው ትልቅ ሰውዬ ነው።
"አላውቅህም!" አልኩት እንደሚሰማኝ ሳረጋግጥ፡፡
“እኔን ማወቅሽ አይደለም እዚህ ያመጣኝ ማወቅ የምትፈልጊውን ነገር እኔ ማወቄ ነው።” ያለኝ በትክክል አልገባኝም፡፡
"እኔ ማወቅ የምፈልገው ነገር የለም።" አልኩት ከሚቀጥለው መልሱ በኋላ ትቼው ልሄድ ራሴን እያሰናዳሁ።
"እናትሽን አውቃታለሁ፡፡ እንዴት እንዳረገዘችሽም አውቃለሁ።"
አለ ስሜቴን ከፊቴ ላይ እየበረበረ::
"ማወቅ አልፈልግም። ጥያቄዬን ከእርሷ ጋር አብሬ ገድዬዋለሁ።" ብዬው እየሸሸሁ መሆኔ እየታወቀኝ ጥዬው ለመሄድ ዞርኩ፡፡
"ከማን እንደወለደችሽስ ማወቅ አትፈልጊም?" ቀጥ አልኩ።ምንም ያህል ብታገል አባቴን ለማወቅ የሚላወሰውን ፍላጎቴን መገደብ አቃተኝ። ተመልሼ አጠገቡ ደረስኩ።
"እናትሽን በአንቺ እጅ ተገድላ መሞቷን ስሰማ የነበራችሁን ግንኙነት ማጣራት ጀመርኩ። ላንቺ፣ ለእናትሽ፣ ለራሴ
ማናችንን ነፃ እንደሚያወጣ ባላውቅም እውነቱን ልነግርሽ እንደሚገባ ወሰንኩ።" መጨማደድ የጀመረ ግንባሩን እያኮራመተ ይለጥጣል፡፡ የወሬ ማጀቢያው ትዕግስቴን እየተፈታተነው ነበር፡፡
ቀጥታ መልሱን ንገረኝ አባቴ ማን ነው?"
"እናትሽ እስር ቤት ውስጥ ተደፍራ ነው ያረገዘችሽ፡፡ ቁጥራቸው የማይታወቅ ጠባቂዎች ናቸው የደፈሯት። የማንኛው ልጅ መሆንሽ አይታወቅም፡፡ በወቅቱ እዛ ፖሊስ ነበርኩ፡፡ ስናገኛት ራሷን አታውቅም ነበር፡፡ ለወራት ስትታከም ቆይታ ነው
የዳነችው። ከባድ ስቃይ ብታልፍም የአካል ቁስሏን ድናለች።ከዛን ዕለት በኋላ ክንፏን የተሰበረች ወፍ ሆነች:: ......"
ማውራቱን ቀጥሏል... ጥዬው ገብቻለሁ።
💫ተ..ፈ..ፀ..መ💫
Like 👍 #Share እያደረጋቹ ይሄ ቢያልቅ ሌላ እንጀምራለን ግን የናንተ አስተያየት ወሳኝ ነው ስለ ድርሰቱ ስለ ቻናላችን ምን ይጨመር? ምን ይቀነስ? ያላችሁን አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን። አመሰግናለው🙏
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት (የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
...ሰላም?” አልኩኝ የማውቀው ፊት ላይ አፍጥጬ።ብዙም ደቂቃ አላባከኑም ወንዶቹ ወንድሞቼ መሆናቸውንና ሴቶቹ
ፍቅረኞቻቸው መሆናቸውን ሲነግሩኝ አልጋ ላይ ሆኜ እየቃዠሁ አለመሆኔን ደጋግሜ ራሴን ስጠይቀው:: ለምን ነበር ወንድሜ መሆኑን እንዳውቅ ያልፈለገችው? ይህቺ ሴትዮ በስንቱ ነው
የምትበድለኝ? ስትሞት ጥያቄዬ ሁሉ አብሯት የሞተና ከዚያ በኋላ መቼም የማያስጨንቀኝ መስሎኝ ነበር፡፡ ነገር
ግን በተቃራኒው ሆነ፡፡ ሞታም ይኸው ግራ እያጋባች ታቀውሰኛለች።
ከተለያየ ወንዶች የወለደቻቸው ሁለት
ወንድሞች አሉኝ፡፡ ምናልባት ሌሎችም ይኖሩ ይሆናል፡፡ምክንያቱም እነርሱም እህት እንዳላቸው ያወቁት ስለገደልኳት
ነው። ሴትየዋ ማን ነበረች? ምንስ ነበር ትርፏ?
ብዙ ዓረፍተ ነገሮች ሳያባክኑ የተረዳሁት ለእነርሱም ጥሩ እናት እንዳልነበረች ነው። ከፍቅራቸው ገዝፎ ጥላቻና መከፋታቸው
ይታያል። ክልሱ ወንድሜ (ኪሩቤል) በተሻለ ፍቅር ነበረው። ስለገደልኳትም ማዘኑን አልደበቀኝም። ታላቃቸው ነኝ
ኪሩቤልን በሶስት ዓመት እበልጠዋለሁ። ቅዱስን በአስራ አንድ ዓመት።
እየተቅለበለበች የምታወራው የቅዱስ ፍቅረኛ በምሰማው ነገር እየተሰማኝ የነበረውን ስሜት ውል መያዝ
እንዳልችል ታስፎርሸኛለች፡፡ የራሷንም የእርሱንም ደምራ በሚቅበጠበጠው መላ አካሏ እየታጀበች የምታወራው እርሷ
ናት። አንዲትም ቃል ሳልተነፍስ የመጠየቂያ ሰዓቱ አልቆ ከመግባቴ በፊት ኪሩቤል እግሩ ስር አስቀምጦት የነበረውን ካርቶን እየሰጠኝ ይሄ አንቺ ትፅፊላት የነበሩት ደብዳቤዎች ናቸው። ከአጠገቧ ተለይቷት አያውቅም። ሆስፒታል እንኳን አብረዋት ነበሩ።
ያንቺ መሆኑን ያወቅነው ከሞተች በኋላ
ነው። ለነዚህ ደብዳቤዎች ፍቅር እንደነበራት አውቃለሁ። እያነበበች
ትንሰቀሰቅ ነበር። ምናልባት የምትፈልጊው ከሆነ ብለን ነው።"
አለኝ፡፡ የነገረኝ ነገር እኔ ውስጥ የሚፈጥረውን ውስብስብ ሳይረዳ፡፡
"ከእኔ ከልጇ በላይ አንቺ የምትፅፊላት ደብዳቤ ትርጉም ነበረው።ማን መሆንሽን ሳላውቅ ብዙ ጊዜ ቀንቼብሻለሁ::" አለ እስካሁን ከንግግር የተቆጠበው ቅዱስ፡፡ በስልክ ላገኛት ባለመቻሌ እቤቷ የሄድኩ ጊዜ ባሏ ነበረ የፖስታ አድራሻዋን የስጠኝ፡፡ ታንብበው አታንብበው እንኳን ሳላውቅ በየወሩ እፅፍላት ነበር፡፡ አንዳንዴ
ባታነበው እንኳን የውስጤን እየተነፈስኩ ስለሚመስለኝ መፃፌን አላቆምም ነበር። ስለእርሷ ለመርሳት መሞከር በጀመርኩ ጊዜ ከጥቂት ዓመታት በፊት ነው መፃፌን ያቋረጥኩት፡፡ተሰናብተውኝ ከሄዱ በኋላ ምን ማሰብና የቱን ማመን እንዳለብኝ
ግራ ተጋባሁ። ትወደኝ ነበር? ትጠላኝ ነበር? ትፀፀት ነበር? የትኛው ነበር ልኩ? የምታሳየኝ ጥላቻ ወይስ የደበቀችኝ ፀፀት?ለቀናት በጥቅጥቅ የጥያቄ ጫካ ውስጥ ተቅበዘበዝኩ። ጠፋሁ። መውጫው የማይገኝ ሆኖብኝ ባተትኩ። ማን ነበረች ይህቺ ሴትዮ?
ኪሩቤል አዘውትሮ መምጣቱን በቀጠለ መጠን ስለእርሷ የሚነግረኝ ነገር ሌላ የማላውቀው የእርሷ ገፅታ ነው።ሁሌም
በመጣ ቁጥር በሞቷ እናቱን እንዳሳጣሁት ይወቅሰኝ ስለነበር
በአንዱ ቀን የበደሌን ግዝፈት ልከምርለት አፌን ለማላቀቅ ተገደድኩ፡፡ የረጋ ቀልብ ያላት ፍቅረኛው በእንባዬ ጠብታ ልክ
እንባዋን እያፈሰሰች ስትሰማኝ እርሱ በጭንቀት ሲንቆራጠጥ ቆይቶ ምንም ቃል ሳይተነፍስ ሄደ፡፡ ለወቀሳው የመጨረሻ ቀን ሆነ፡፡ በፍቅረኛው ተገዶ የሚመጣ የሚመስለኝ ቅዱስ አልፎ
አልፎ ቢመጣም እርሷ ታወራለታለች እንጂ በዝምታ ሰዓቱን ጨረሶ ነበር የሚሰናበተኝ። በቃላት ባይናገረውም አምርሮ እንደሚጠላት መደበቅ አይችልም።የሁሉም ዑደት አንድ ጫፍ ላይ ገተረኝ ማናችንም ሴትየዋን አናውቃትም ልናውቃትም አንችልም። እንቆቅልሽ ነበረች:ፈ።ከነእንቆቅልሿ ተቀብራለች።ይሄን እያሰብኩ የእስር ቤት ቀኖቼን ልረሳት እራሴን እመክራለሁ፡፡ ወንድሞቼ እና ፍቅረኞቻቸው ሲመጡ ወጥቼ ሳገኛቸው ስለእነርሱ የሚሰማኝን ስሜት እፈትሻለሁ። በየእለቱ ተፈሪ ሊጎበኘኝ ሲመጣ አግብቶ እንዲወልድ እነግረዋለሁ።የታሰርኩ ሰሞን በየእለቱ፣ ጊዜው ሲገፋፋ በሁለት ቀን፣ ሲዘገይ
በሳምንት፣ ከራርሞ በወር፣ ሰነባብቶ ጭራሹኑ ቀረ።
ከእያንዳንዱ ክፋት ጀርባ መሪር በደል አለ እያልኩ አስባለሁ።ጥያቄው የሚሆነው በደልን ይቅር ያለ በጎነት የለም ወይ?
የሚለው ነው። ኖሮ ያውቅ ይሆናል፡ በደልን ይቅር ለማለት የሚያስችል ትልቅ በጎነት የሚፈጥር ፍቅር የሚጠይቅ
ይመስለኛል። የገባኝ በዛ መጠን በልቤ የተንሰራፋ መልካምነት መፍጠር የሚችል ከተበደልኩት ልቆ የሚገዝፍ ፍቅር የለኝም። እናቴን ልገድልበት የቻልኩበትን ቅፅበት ሳስብ በሰውኛ ምክንያት
ከመግመድ አይሎ ቅፅበታዊ ስሜት መላው አካላችንን የሚያዝበት አጋጣሚ መኖሩን ነው። ከታሰርኩ ከብዙ ወራት
በኋላ ጠየቂ እንደመጣልኝ ፖሊሷ ነገረችኝ፡፡ ከወንድሞቼ አንዳቸው እንደሚሆኑ እያሰብኩ ስወጣ ፖሊሷ የጠቆመችኝ ያለዛሬ አይቼ የማላውቀው ትልቅ ሰውዬ ነው።
"አላውቅህም!" አልኩት እንደሚሰማኝ ሳረጋግጥ፡፡
“እኔን ማወቅሽ አይደለም እዚህ ያመጣኝ ማወቅ የምትፈልጊውን ነገር እኔ ማወቄ ነው።” ያለኝ በትክክል አልገባኝም፡፡
"እኔ ማወቅ የምፈልገው ነገር የለም።" አልኩት ከሚቀጥለው መልሱ በኋላ ትቼው ልሄድ ራሴን እያሰናዳሁ።
"እናትሽን አውቃታለሁ፡፡ እንዴት እንዳረገዘችሽም አውቃለሁ።"
አለ ስሜቴን ከፊቴ ላይ እየበረበረ::
"ማወቅ አልፈልግም። ጥያቄዬን ከእርሷ ጋር አብሬ ገድዬዋለሁ።" ብዬው እየሸሸሁ መሆኔ እየታወቀኝ ጥዬው ለመሄድ ዞርኩ፡፡
"ከማን እንደወለደችሽስ ማወቅ አትፈልጊም?" ቀጥ አልኩ።ምንም ያህል ብታገል አባቴን ለማወቅ የሚላወሰውን ፍላጎቴን መገደብ አቃተኝ። ተመልሼ አጠገቡ ደረስኩ።
"እናትሽን በአንቺ እጅ ተገድላ መሞቷን ስሰማ የነበራችሁን ግንኙነት ማጣራት ጀመርኩ። ላንቺ፣ ለእናትሽ፣ ለራሴ
ማናችንን ነፃ እንደሚያወጣ ባላውቅም እውነቱን ልነግርሽ እንደሚገባ ወሰንኩ።" መጨማደድ የጀመረ ግንባሩን እያኮራመተ ይለጥጣል፡፡ የወሬ ማጀቢያው ትዕግስቴን እየተፈታተነው ነበር፡፡
ቀጥታ መልሱን ንገረኝ አባቴ ማን ነው?"
"እናትሽ እስር ቤት ውስጥ ተደፍራ ነው ያረገዘችሽ፡፡ ቁጥራቸው የማይታወቅ ጠባቂዎች ናቸው የደፈሯት። የማንኛው ልጅ መሆንሽ አይታወቅም፡፡ በወቅቱ እዛ ፖሊስ ነበርኩ፡፡ ስናገኛት ራሷን አታውቅም ነበር፡፡ ለወራት ስትታከም ቆይታ ነው
የዳነችው። ከባድ ስቃይ ብታልፍም የአካል ቁስሏን ድናለች።ከዛን ዕለት በኋላ ክንፏን የተሰበረች ወፍ ሆነች:: ......"
ማውራቱን ቀጥሏል... ጥዬው ገብቻለሁ።
💫ተ..ፈ..ፀ..መ💫
Like 👍 #Share እያደረጋቹ ይሄ ቢያልቅ ሌላ እንጀምራለን ግን የናንተ አስተያየት ወሳኝ ነው ስለ ድርሰቱ ስለ ቻናላችን ምን ይጨመር? ምን ይቀነስ? ያላችሁን አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን። አመሰግናለው🙏
👍5