#ለሕዝቡ_ብሎ
ምነው ገለሌ
ምነው ገለሌ
አመሉ ቅጥፈት፣ ስሙም እገሌ
በከፊል መናኝ፣ ግማሽ ተጋዳይ
የማጀቱን ጉድ፣ የራሱን ጉዳይ
ከድኖ በማብሰል
ባገሩ ጣጣ፣ የሚብሰለሰል
ስብከት በጉንጩ
የግሣፄና የርግማን ምንጩ።
ፍሬ ከርስኪው የማይጠገብ
ካልጋው አጠገብ
ዘብ ቆሞ አዳሪው
ቆሪጥ ወታደር
ተልኮው ጥሪው
በካሜራ ፊት ሲያወራ ማደር።
ቢያምር ባያምር፣ ቢጣፍጥ ባይጥም
ካሜራና ጅል፣ ትይንት አይመርጥም።
በቅሎ አትሸልሙት
ፈረስ አትጫኑ
ፈረስ እኮ ነው የገዛ ጭኑ
ካንደኛው ዜጋ ወዳንዱ ዜጋ
እየጋለበ
በሀሜት ዘገር በስድብ ሎጋ
እያካለበ
የሚዋደቅ ነው በየስክሪኑ
በላፕቶፑ ላይ ሰርክ ተጥዶ
አንድ ሺ ዘልፎ
አንድ ሺ አዋርዶ
ዘመን የጣላት
ዘመድ የጠላት
ባልቴት ይመስል
ስድብ ሲቀቅል
ነገር ሲያማስል
ሲያማርር ውሎ
ለሕዝቡ ብሎ
ካልጋው ተነስቶ ፍሪጁ ድረስ
ጊዜ እያጠረው አይንቀሳቀስ
ለሕዝቡ ብሎ። .
ምነው ገለሌ
ምነው ገለሌ
አመሉ ቅጥፈት፣ ስሙም እገሌ
በከፊል መናኝ፣ ግማሽ ተጋዳይ
የማጀቱን ጉድ፣ የራሱን ጉዳይ
ከድኖ በማብሰል
ባገሩ ጣጣ፣ የሚብሰለሰል
ስብከት በጉንጩ
የግሣፄና የርግማን ምንጩ።
ፍሬ ከርስኪው የማይጠገብ
ካልጋው አጠገብ
ዘብ ቆሞ አዳሪው
ቆሪጥ ወታደር
ተልኮው ጥሪው
በካሜራ ፊት ሲያወራ ማደር።
ቢያምር ባያምር፣ ቢጣፍጥ ባይጥም
ካሜራና ጅል፣ ትይንት አይመርጥም።
በቅሎ አትሸልሙት
ፈረስ አትጫኑ
ፈረስ እኮ ነው የገዛ ጭኑ
ካንደኛው ዜጋ ወዳንዱ ዜጋ
እየጋለበ
በሀሜት ዘገር በስድብ ሎጋ
እያካለበ
የሚዋደቅ ነው በየስክሪኑ
በላፕቶፑ ላይ ሰርክ ተጥዶ
አንድ ሺ ዘልፎ
አንድ ሺ አዋርዶ
ዘመን የጣላት
ዘመድ የጠላት
ባልቴት ይመስል
ስድብ ሲቀቅል
ነገር ሲያማስል
ሲያማርር ውሎ
ለሕዝቡ ብሎ
ካልጋው ተነስቶ ፍሪጁ ድረስ
ጊዜ እያጠረው አይንቀሳቀስ
ለሕዝቡ ብሎ። .
#ቀላውጦ_ማስመለስ
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
ትለኛለች።እውነቱን ሳወራት ይከፋታል። አኮረፈች። ጥላኝ ግን አልሄደችም።
"አንተጋ ልደር?” አለችኝ፡፡“
“ደስ ይለኛል!” አልኳት እንድትሄድ አልፈለግኩም፡፡
“የት እተኛለሁ?”
"የተመቸሽ ቦታ"
የተመቻት ቦታ ከኔጋ አልጋዬ ላይ መተኛት ነበር፡፡ እንደዛ አደረገች፡፡ እንደብዙ ነገር አደረገች፡፡ ልብሶቼን ከላዬ እንዴት ገፋ
ጣለቻቸው? ከመቼው አልጋው ላይ ወደቅን?ከላዬ ነበረች? በየትኛው ቅፅበት ከስሬ አገኘኋት? የማላውቃት የሆነች ልጅ ነበረች፡፡ የደስታ ሲቃዬን ያበዛችው ግን የማላውቃት ባዕድ ነገር የሆነችብኝ፡፡ ከሰውነቴ አጣብቄ እንዳቀፍኳት ነጋ፡፡
“አትሂጂ አብረሽኝ ኑሪ!” አልኳት፡፡
ትወደኛለህ?” ብላ ጠየቀችኝ።
“እኔንጃ!” መለስኩላት።
ከእናቷ ጋር ብዙ ከተነታረከች በኋላ አብራኝ መኖር ጀመረች፡፡ልክ ያልሆነ ነገር ያለው አኗኗር መሆኑ ይገባኛል፡፡ አብራኝ
ልትኖር የወሰነች ቀን ማታ በድጋሚ “ትወደኛለህ ወይ?” ብላ ጠየቀችኝ፡፡ በማላውቀው ምክንያት ይሄ ጥያቄዋ የሚከብድ ነገር አለው፡፡ መውደድ፣ ናፍቆት፣ ፍቅር ዓይነት ላሉ ስሜቶች
እርግጠኛነቴን እንጃ፡፡ ስሜቱ ምን ስለመምሰሉም አላውቅም።
“ስትስሚኝ ደስ ይለኛል፡ ባለፈው ዕለት እንትን ስናደርግም በጣም ነው ደስ ያለኝ።
“አብሮ ለመኖር ይሄ በቂ አይደለም፡፡ ፍቅር ነው ዋናው! እንደወደድከኝ እስኪሰማህ ድረስ አብሬህ እሆናለሁ፡፡ ነገር ግን ምንም አናደርግም፡፡” ያለችው ምን ያህሉ እንደገባኝ አልገባኝም፡፡
“ቆይ አንቺ ስናደርግ ደስ አላለሽም ነበር?”
“ፍቅር የሌለበት ወሲብ ማድረግ አልፈልግም፡፡” የምጠይቃትና
የምትመልስልኝ አልገጣጠም ይለኛል፡፡ እኔ እስከገባኝ ያደረግነው የሁለታችንም ደስታ የነበረበት ነገር ነበር፡፡ ብቻዬን ያደረግኩ፣ደስታው የእኔ ብቻ እንደነበር፣ እርካታው የግሌ ብቻ እንደሆነ እንዲሰማኝ ለምን እንደምታደርግ አይገባኝም፡፡ እንድዋሻት ትፈልጋለች፡፡ ምክንያቱም ራስዋን መዋሸት ስለምትፈልግ።በፍቅር ስም ለፍቅር ብላ ጭኖቿን እንደከፈተችልኝ እንጂ ለስሜትዋና ለደስታዋ ስትል ከማይወዳት ወንድ ጋር እንዳደረገችው በማሰብ ለራሷ ያላትን ግምት ዝቅ ማድረግ አትፈልግም፡፡ ደስታን መፈለግ ክፋቱ አይገባኝም፡፡ ለምን ሌላ ምክንያት ይለጠፍበታል? ለሁለት ወራት እንደዚህ አብረን ከኖርን በኋላ ነበር ህልሟን የነገረችኝ፡፡ ከፈቃዱ ጋር የሰራችውን የህልም ፍቅር!
በመላኩ ምክር ቅደም ተከተል መሰረት ከመተኛቴ በፊት አንዲት ፍቅረኛዬ የምታደንቃትን ታዋቂ ሴት አርቲስት ገላ ለማሰብ ሞከርኩ፡፡ከፍቅረኛዬ ውጪ የማንም ሴት ገላ ሊከሰትልኝ አልቻለም፡፡ ከዛሬ ሁለት ወር በፊት ለመጀመሪያም ለመጨረሻም ጊዜ ከላዬ ሆና ዛር እንዳለበት ሰው ካበደችው እብደት ውጪ
ምንም ወደ ሀሳቤ ሊመጣልኝ አልቻለም፡፡ በእርግጥ እንዴትስ ማሰብ ይቻለኝ ነበር? ከሷ ውጪ የሴት እርቃን በፊልም እንኳን
ማየቴ ትዝ አይለኝም፡፡ ያየኋቸውን በአንድ የእጅ ጣት የሚቆጠሩ ፊልሞችም እሷው ናት ያሳየችኝ፡፡ ሴቶቹ ልብሳቸውን አውልቀው የሚያሳይ ቦታ ነበረው? አላስታውስም፡፡
“እ? ተሳካልሽ? ማታ ቺኳ ከች አለች?” አለኝ መላኩ ሱቄን ጠዋት እንደከፈትኩ ለወሬ ቸኩሎ።
“አላለችም ::አንተ ነህ ከች ያልክብኝ!! አልኩት መናደዴን እንዲያውቅ ጥርሴን ነክሼ።ላለመሳቅ እየታገለ።
“ምን ሳደርግ?” አለኝ።
“ብዙውን አላስታውስም፡፡ በጥፊ ስታልሰኝ ነው ከእንቅልፌ የባነንኩት” ስለው እስኪበቃው አገጠጠ፡፡ በህልሜ ረድኤትን የማስቀናቱ ሀሳብ አልተሳካልኝም።
“መነጋገር አለብን!” አልኳት አዋርቻት በማላውቀው ድምፀት፡፡ስታወራ እሰማታለሁ እንጂ ራሴ ርዕስ ፈጥሬ አዋርቻት አላውቅም።
"ዛሬ ወለላን ሄደን መጠየቅ አለብን።" አለችኝ ያልኳትን እንዳልሰማች ሁሉ ርዕስ ቀይራ:: ትናንትና ከሰዓት የወለላ ነፍስ
አባት እቤት ድረስ መጥተው ጉበቷ አደገኛ ደረጃ ላይ ስለደረስ ከማገገሚያ ወጥታ ከፍተኛ ሆስፒታል ከተኛች መክረሟን ከነገሩን ሰዓት ጀምሮ በዚህ ጉዳይ ፀብ ቀረሽ ንትርክ ላይ ነን፡፡
እኔ እናቴን ላያት አልፈልግም፡፡ እርሷ ደግሞ ምንም ቢሆን እናቴ ስለሆነች የኛ ጥየቃ ይገባታል እያላች ችክ ብላለች። እኔ
ላናግራት የፈለግኩት በየእርምጃዬ ልረሳው ስላልቻልኩት ህልሜ ነበር። ጭቅጭቋ ሊያሳብደኝ ስለደረሰ ቁርስ እንደበላን ሆስፒታል ሄድን፡፡ ወለላ ጉዷ ተጎትቶ የማያልቅ ሴት መሆኗን ባውቅም
ለአፍታ ሽው ባለች ቅፅበት አስቤው የማላውቀው ነገር ገጠመኝ።
የወለላ ልጅ የእኔ ታላቅ ወንድም ሲያስታምማት አገኘሁት፡፡የተፈጠረው ነገር የሆነ የተልወሰወሰ ነገር አለው። መቼ ነው የወለደችው? አላሳደገችውም ማለት ነው? ለነገሩ ተገላገለ ከድብደባ ነው የተረፈው። ያላሳደገችውን እናቱን እንዴት እናቴ ብሎ ይጠራታል? እንዴትስ እያደረ ያስታምማታል? ይሄን
የማስበው የወለላ ልጅ መሆኑን በነገረኝ ቅፅበት ረድኤት እየተውረገረገች ወንድሙ መሆኔን ስትነግረው እርሱም እልፍ እያሰበ በመሰለኝ ሽርፍራፊ የጊዜ ክፍተት ነው። ምክንያቱም እሱም ወንድም እንዳለው አያውቅም። እርሱ ዝም አላለም።የሰማው ነገር ልክ መሆኑን ሲያረጋግጥ እድሜዬን ጠየቀኝ እና
ከራሱ ጋር ማስላት ጀመረ። በስምንት ዓመት እንደሚበልጠኝ ነገረኝ። ስራ እንዳለበት ነግሮን ሲወጣ አንድ ጥያቄ ብቻ ጠየቅኩት።
"ደብዳቤ የምትፅፍላት አንተ ነበርክ?" በመገረም እያስተዋለኝ አለመሆኑን ነግሮኝ ወጣ: ወንድም ማግኘቴ ከመገረም ልቆ የሰጠኝን ስሜት አላወቅኩትም።ወንድሜ ጥሩ ሰው ይመስላል፡፡ወለላን መውደዱን ግን ማመን አልቻልኩም። ረድኤት ከስራ
እስክትመለስ ሱቅ ቆሜ በሀሳብ እዚህ እዚያ ስረግጥ ዋልኩኝ።ዛሬ ሳላናግራት አላድርም እያልኩ ስዝት ውዬ መጣች።
“ጠዋት ስለምን ነበር ልታወራኝ የነበረው?” አለችኝ እራት የበላንበትን ሰሃን እያነሳሳች።
“እየቀናሁ ነው!” አልኳት፡፡
“አልገባኝም!!” አለችኝ የያዘችውን ሰሃን መልሳ እያስቀመጠች።
“አየሁት ካልሽኝ ህልም ውጪ ምንም ማሰብ አልቻልኩም፡፡”ስላት ሳቀች፡፡ ከት ብላ ሳቀች፡፡
“ጅል ነህ! ጅልነትህን ግን እወደዋለሁ፡፡"
“ጅል አትበይኝ! አትበይኝ በቃ!! የኔ ብቻ እንድትሆኚ መፈለግ ጅልነት ነው? ሌላ ሰው እንዳይነካብኝ መሳሳት ጅልነት ነው?
ስራ ውለሽ እስክትመጪ ላይሽ መጓጓቴ ነው ጅልነት? አቅፌሽ እያደርኩ ለራሴ ስሜት ሳይሆን ላንቺ ቃል መጠንቀቄ ጅልነት ነው? የቱ ነው ጅልነት? ከንፈርሽን መናፈቄ ነው ጅልነት?ንገሪኝ ይሄ ጅልነት ነው?” እንደዚህ መናገር መቻሌን ያወቅኩት ዛሬ ነው።
“አይደለም፡፡” አለችኝ እኔ ከምናገርበት የቁጣ ጩኸት ተቃራኒ በሆነ ለስላሳ አንደበት፡፡
“ይሄ ጅልነት አይደለም ፍቅር ነው ማሬ” አለችኝ፡፡ በፈገግታዋ መሃል ዓይኖቿ እንባ ሲያረግዙ አየኋቸው፡፡ ሳማት ሳማት
የሚለኝን ስሜቴን ማቆም አልቻልኩም። ከማድረጌ ቀድሞ ግን ስልኬ ጠራ! ወንድሜ ነው:: ዛሬ ጠዋት አውቆኝ ፍቅር ፍቅር ሊጫወት ከሆነ እየተገረምኩ ዝም ብዬ ስልኩን አየዋለሁ።የማንሳት ጉጉት አልነበረኝም።ረድኤት እንዳነሳው ስትነግረኝ ግን አነሳሁት፡፡ ምንድነው ያለኝ?
"ስህተት እናታችን ሞታለች:: ማለቴ ተገድላለች::"ሲለኝ መሞቷ አልገረመኝም: አላሳዘነኝምም:: አሟሟቷ እንጂ!
ወለላ እኔን ስትቀጠቅጥ እና ባሎች አግብታ ስትፈታ ኖራ......ኖራ......... ኖራ........ የረሳሁላት ከፍተኛ ምግባር አለ፡፡ስትራገም ኖራ ኖራ....... በተጨማሪ ደብዳቤ ስታነብ ኖራ...ኖራ... ለእኔ የማያልቅ ከሚመስል ዘመን በኋላ በሀያ ሁለት ዓመቴ ሞተች፡፡ እሰይ ሞተች!
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
ትለኛለች።እውነቱን ሳወራት ይከፋታል። አኮረፈች። ጥላኝ ግን አልሄደችም።
"አንተጋ ልደር?” አለችኝ፡፡“
“ደስ ይለኛል!” አልኳት እንድትሄድ አልፈለግኩም፡፡
“የት እተኛለሁ?”
"የተመቸሽ ቦታ"
የተመቻት ቦታ ከኔጋ አልጋዬ ላይ መተኛት ነበር፡፡ እንደዛ አደረገች፡፡ እንደብዙ ነገር አደረገች፡፡ ልብሶቼን ከላዬ እንዴት ገፋ
ጣለቻቸው? ከመቼው አልጋው ላይ ወደቅን?ከላዬ ነበረች? በየትኛው ቅፅበት ከስሬ አገኘኋት? የማላውቃት የሆነች ልጅ ነበረች፡፡ የደስታ ሲቃዬን ያበዛችው ግን የማላውቃት ባዕድ ነገር የሆነችብኝ፡፡ ከሰውነቴ አጣብቄ እንዳቀፍኳት ነጋ፡፡
“አትሂጂ አብረሽኝ ኑሪ!” አልኳት፡፡
ትወደኛለህ?” ብላ ጠየቀችኝ።
“እኔንጃ!” መለስኩላት።
ከእናቷ ጋር ብዙ ከተነታረከች በኋላ አብራኝ መኖር ጀመረች፡፡ልክ ያልሆነ ነገር ያለው አኗኗር መሆኑ ይገባኛል፡፡ አብራኝ
ልትኖር የወሰነች ቀን ማታ በድጋሚ “ትወደኛለህ ወይ?” ብላ ጠየቀችኝ፡፡ በማላውቀው ምክንያት ይሄ ጥያቄዋ የሚከብድ ነገር አለው፡፡ መውደድ፣ ናፍቆት፣ ፍቅር ዓይነት ላሉ ስሜቶች
እርግጠኛነቴን እንጃ፡፡ ስሜቱ ምን ስለመምሰሉም አላውቅም።
“ስትስሚኝ ደስ ይለኛል፡ ባለፈው ዕለት እንትን ስናደርግም በጣም ነው ደስ ያለኝ።
“አብሮ ለመኖር ይሄ በቂ አይደለም፡፡ ፍቅር ነው ዋናው! እንደወደድከኝ እስኪሰማህ ድረስ አብሬህ እሆናለሁ፡፡ ነገር ግን ምንም አናደርግም፡፡” ያለችው ምን ያህሉ እንደገባኝ አልገባኝም፡፡
“ቆይ አንቺ ስናደርግ ደስ አላለሽም ነበር?”
“ፍቅር የሌለበት ወሲብ ማድረግ አልፈልግም፡፡” የምጠይቃትና
የምትመልስልኝ አልገጣጠም ይለኛል፡፡ እኔ እስከገባኝ ያደረግነው የሁለታችንም ደስታ የነበረበት ነገር ነበር፡፡ ብቻዬን ያደረግኩ፣ደስታው የእኔ ብቻ እንደነበር፣ እርካታው የግሌ ብቻ እንደሆነ እንዲሰማኝ ለምን እንደምታደርግ አይገባኝም፡፡ እንድዋሻት ትፈልጋለች፡፡ ምክንያቱም ራስዋን መዋሸት ስለምትፈልግ።በፍቅር ስም ለፍቅር ብላ ጭኖቿን እንደከፈተችልኝ እንጂ ለስሜትዋና ለደስታዋ ስትል ከማይወዳት ወንድ ጋር እንዳደረገችው በማሰብ ለራሷ ያላትን ግምት ዝቅ ማድረግ አትፈልግም፡፡ ደስታን መፈለግ ክፋቱ አይገባኝም፡፡ ለምን ሌላ ምክንያት ይለጠፍበታል? ለሁለት ወራት እንደዚህ አብረን ከኖርን በኋላ ነበር ህልሟን የነገረችኝ፡፡ ከፈቃዱ ጋር የሰራችውን የህልም ፍቅር!
በመላኩ ምክር ቅደም ተከተል መሰረት ከመተኛቴ በፊት አንዲት ፍቅረኛዬ የምታደንቃትን ታዋቂ ሴት አርቲስት ገላ ለማሰብ ሞከርኩ፡፡ከፍቅረኛዬ ውጪ የማንም ሴት ገላ ሊከሰትልኝ አልቻለም፡፡ ከዛሬ ሁለት ወር በፊት ለመጀመሪያም ለመጨረሻም ጊዜ ከላዬ ሆና ዛር እንዳለበት ሰው ካበደችው እብደት ውጪ
ምንም ወደ ሀሳቤ ሊመጣልኝ አልቻለም፡፡ በእርግጥ እንዴትስ ማሰብ ይቻለኝ ነበር? ከሷ ውጪ የሴት እርቃን በፊልም እንኳን
ማየቴ ትዝ አይለኝም፡፡ ያየኋቸውን በአንድ የእጅ ጣት የሚቆጠሩ ፊልሞችም እሷው ናት ያሳየችኝ፡፡ ሴቶቹ ልብሳቸውን አውልቀው የሚያሳይ ቦታ ነበረው? አላስታውስም፡፡
“እ? ተሳካልሽ? ማታ ቺኳ ከች አለች?” አለኝ መላኩ ሱቄን ጠዋት እንደከፈትኩ ለወሬ ቸኩሎ።
“አላለችም ::አንተ ነህ ከች ያልክብኝ!! አልኩት መናደዴን እንዲያውቅ ጥርሴን ነክሼ።ላለመሳቅ እየታገለ።
“ምን ሳደርግ?” አለኝ።
“ብዙውን አላስታውስም፡፡ በጥፊ ስታልሰኝ ነው ከእንቅልፌ የባነንኩት” ስለው እስኪበቃው አገጠጠ፡፡ በህልሜ ረድኤትን የማስቀናቱ ሀሳብ አልተሳካልኝም።
“መነጋገር አለብን!” አልኳት አዋርቻት በማላውቀው ድምፀት፡፡ስታወራ እሰማታለሁ እንጂ ራሴ ርዕስ ፈጥሬ አዋርቻት አላውቅም።
"ዛሬ ወለላን ሄደን መጠየቅ አለብን።" አለችኝ ያልኳትን እንዳልሰማች ሁሉ ርዕስ ቀይራ:: ትናንትና ከሰዓት የወለላ ነፍስ
አባት እቤት ድረስ መጥተው ጉበቷ አደገኛ ደረጃ ላይ ስለደረስ ከማገገሚያ ወጥታ ከፍተኛ ሆስፒታል ከተኛች መክረሟን ከነገሩን ሰዓት ጀምሮ በዚህ ጉዳይ ፀብ ቀረሽ ንትርክ ላይ ነን፡፡
እኔ እናቴን ላያት አልፈልግም፡፡ እርሷ ደግሞ ምንም ቢሆን እናቴ ስለሆነች የኛ ጥየቃ ይገባታል እያላች ችክ ብላለች። እኔ
ላናግራት የፈለግኩት በየእርምጃዬ ልረሳው ስላልቻልኩት ህልሜ ነበር። ጭቅጭቋ ሊያሳብደኝ ስለደረሰ ቁርስ እንደበላን ሆስፒታል ሄድን፡፡ ወለላ ጉዷ ተጎትቶ የማያልቅ ሴት መሆኗን ባውቅም
ለአፍታ ሽው ባለች ቅፅበት አስቤው የማላውቀው ነገር ገጠመኝ።
የወለላ ልጅ የእኔ ታላቅ ወንድም ሲያስታምማት አገኘሁት፡፡የተፈጠረው ነገር የሆነ የተልወሰወሰ ነገር አለው። መቼ ነው የወለደችው? አላሳደገችውም ማለት ነው? ለነገሩ ተገላገለ ከድብደባ ነው የተረፈው። ያላሳደገችውን እናቱን እንዴት እናቴ ብሎ ይጠራታል? እንዴትስ እያደረ ያስታምማታል? ይሄን
የማስበው የወለላ ልጅ መሆኑን በነገረኝ ቅፅበት ረድኤት እየተውረገረገች ወንድሙ መሆኔን ስትነግረው እርሱም እልፍ እያሰበ በመሰለኝ ሽርፍራፊ የጊዜ ክፍተት ነው። ምክንያቱም እሱም ወንድም እንዳለው አያውቅም። እርሱ ዝም አላለም።የሰማው ነገር ልክ መሆኑን ሲያረጋግጥ እድሜዬን ጠየቀኝ እና
ከራሱ ጋር ማስላት ጀመረ። በስምንት ዓመት እንደሚበልጠኝ ነገረኝ። ስራ እንዳለበት ነግሮን ሲወጣ አንድ ጥያቄ ብቻ ጠየቅኩት።
"ደብዳቤ የምትፅፍላት አንተ ነበርክ?" በመገረም እያስተዋለኝ አለመሆኑን ነግሮኝ ወጣ: ወንድም ማግኘቴ ከመገረም ልቆ የሰጠኝን ስሜት አላወቅኩትም።ወንድሜ ጥሩ ሰው ይመስላል፡፡ወለላን መውደዱን ግን ማመን አልቻልኩም። ረድኤት ከስራ
እስክትመለስ ሱቅ ቆሜ በሀሳብ እዚህ እዚያ ስረግጥ ዋልኩኝ።ዛሬ ሳላናግራት አላድርም እያልኩ ስዝት ውዬ መጣች።
“ጠዋት ስለምን ነበር ልታወራኝ የነበረው?” አለችኝ እራት የበላንበትን ሰሃን እያነሳሳች።
“እየቀናሁ ነው!” አልኳት፡፡
“አልገባኝም!!” አለችኝ የያዘችውን ሰሃን መልሳ እያስቀመጠች።
“አየሁት ካልሽኝ ህልም ውጪ ምንም ማሰብ አልቻልኩም፡፡”ስላት ሳቀች፡፡ ከት ብላ ሳቀች፡፡
“ጅል ነህ! ጅልነትህን ግን እወደዋለሁ፡፡"
“ጅል አትበይኝ! አትበይኝ በቃ!! የኔ ብቻ እንድትሆኚ መፈለግ ጅልነት ነው? ሌላ ሰው እንዳይነካብኝ መሳሳት ጅልነት ነው?
ስራ ውለሽ እስክትመጪ ላይሽ መጓጓቴ ነው ጅልነት? አቅፌሽ እያደርኩ ለራሴ ስሜት ሳይሆን ላንቺ ቃል መጠንቀቄ ጅልነት ነው? የቱ ነው ጅልነት? ከንፈርሽን መናፈቄ ነው ጅልነት?ንገሪኝ ይሄ ጅልነት ነው?” እንደዚህ መናገር መቻሌን ያወቅኩት ዛሬ ነው።
“አይደለም፡፡” አለችኝ እኔ ከምናገርበት የቁጣ ጩኸት ተቃራኒ በሆነ ለስላሳ አንደበት፡፡
“ይሄ ጅልነት አይደለም ፍቅር ነው ማሬ” አለችኝ፡፡ በፈገግታዋ መሃል ዓይኖቿ እንባ ሲያረግዙ አየኋቸው፡፡ ሳማት ሳማት
የሚለኝን ስሜቴን ማቆም አልቻልኩም። ከማድረጌ ቀድሞ ግን ስልኬ ጠራ! ወንድሜ ነው:: ዛሬ ጠዋት አውቆኝ ፍቅር ፍቅር ሊጫወት ከሆነ እየተገረምኩ ዝም ብዬ ስልኩን አየዋለሁ።የማንሳት ጉጉት አልነበረኝም።ረድኤት እንዳነሳው ስትነግረኝ ግን አነሳሁት፡፡ ምንድነው ያለኝ?
"ስህተት እናታችን ሞታለች:: ማለቴ ተገድላለች::"ሲለኝ መሞቷ አልገረመኝም: አላሳዘነኝምም:: አሟሟቷ እንጂ!
ወለላ እኔን ስትቀጠቅጥ እና ባሎች አግብታ ስትፈታ ኖራ......ኖራ......... ኖራ........ የረሳሁላት ከፍተኛ ምግባር አለ፡፡ስትራገም ኖራ ኖራ....... በተጨማሪ ደብዳቤ ስታነብ ኖራ...ኖራ... ለእኔ የማያልቅ ከሚመስል ዘመን በኋላ በሀያ ሁለት ዓመቴ ሞተች፡፡ እሰይ ሞተች!
👍3❤1
“እንደሱ አይባልም!” ትላለች ሌላኛዋ አርጩሜ ረድኤት።
ሰዎች ለምን ይዋሻሉ? ለምንስ እንዲዋሹ ይፈልጋሉ? ማንም የሰፈር ሰው እንደማይወዳት አውቃለሁ፡፡ ታማ ተኝታ መጥተው ሊጠይቋት አልፈቀዱም፡፡ የሞተች ዕለት ለጎረቤቱ መሞቷን
ስነግራቸው ሲያፈቅሯት የኖሩ ያክል፣ ሊያጧት የማይፈልጉ ያህል ሀገር ይያዝ አሉ፡፡ ማንን ነው የሚዋሹት? ከኔ ውጪ
ሊታዘብ የሚችል እነርሱ የሚያውቁት ዘመድ እንደሌላት ያውቃሉ። ምክንያቱም እንኳን የሰፈር ሰው እኔ ራሴ ዘመዶቿን
ያወቅኳቸው ስትሞት ነው። ራሳቸውን ነው የሚዋሹት? ይባስ ብለው እኔም እንድዋሻቸው ይፈልጋሉ፡፡ ረድኤት አባቷ ሲሞት እንዳደረገችው ጉድጓድ ውስጥ ካልገባሁ ብዬ እንድግደረደር
ይጠብቃሉ፡፡ ምን ብዬ ነው የማለቅስላት? ማን ይደብድበኝ? ማን ይስደበኝ? ማን ይርገመኝ? ብዬ? ስለእናቴ ሊመጣልኝ
የሚችለው ምስል ይሄ ብቻ ነው፡፡ ከራሷ ውጪ ማንንም አለመውደዷ፡፡
ከወለላ ሞት በኋላ “አባትህ ነኝ ብሎ አንድ ደልዳላ ሰው መጣ፡፡ወለላን ከፈታ በኋላ ሌላ ቤተሰብ መስርቶ ሶስት ልጆች
መውለዱን ነገረኝ፡፡ ብዙ የምጠይቀው ጥያቄ ቢኖርም አንዱን ብቻ መጠየቅ ቻልኩ።
“ወለላ አንተ ጥላኻት ከመሄድህ በፊት እንዴት ዓይነት ሴት ነበረች?”
“ባወቅካት መንገድ ብቻ እወቃት:: ላንተ እናትህ ናት። ለኔ ሚስቴ ነበረች፡፡ በየቱም መንገድ ወለላ እንደ እናትና እንደ
ሚስት አንድ አይነት ሴት ልትሆን አትችልም፡፡” አለኝ፡፡
“እጅግ እጠላታለሁ!” ያልኩት አስቤው አልነበረም፡፡ ድምፅ ማውጣቴ የገባኝ የእርሱን መደንገጥ ሳይ ነበር፡፡ ብዙ ነገር
የገባው መሰለኝ፡፡ መሰለኝ ብቻ!! ጥሎኝ ከቤት ሲወጣ ተከትዬው ወጣሁ።
“ወለላ እንዳረገዘችህ ሳውቅ ስምህን ቅዱስ ነበር ያልኩህ፡፡ ቅዱስ ጌታነህ” የአባቴን ስም ገና ዛሬ መስማቴ ነው፡፡ ይሄን ብሎኝ የአጥሩን በር ከፍቶ ወጣ፡፡ የእርሱን እግር ተክታ ረድኤት ገባች፡፡
“ማነው?” አለችኝ ።
“አባቴ!” ወደቤት እየገባሁ መለስኩላት፡፡ የምትናገረው ነገር የጠፋባት መሰለኝ፡፡ ሆኖ እንደማያውቀው ለደቂቃዎች ዝም
አለች።
ስሜ ቅዱስ ነበር። ቅዱስ ጌታነህ!" አልኳት። ሰውየው ስሜን ሲነግረኝ የተሰማኝ ስሜት የስም ለውጥ
የተነጠቅኩትን ማንነቴን መልሼ ያገኘሁ ዓይነት እንጂ!! ራሴን የሆንኩ አልመሰለኝም።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
ሰዎች ለምን ይዋሻሉ? ለምንስ እንዲዋሹ ይፈልጋሉ? ማንም የሰፈር ሰው እንደማይወዳት አውቃለሁ፡፡ ታማ ተኝታ መጥተው ሊጠይቋት አልፈቀዱም፡፡ የሞተች ዕለት ለጎረቤቱ መሞቷን
ስነግራቸው ሲያፈቅሯት የኖሩ ያክል፣ ሊያጧት የማይፈልጉ ያህል ሀገር ይያዝ አሉ፡፡ ማንን ነው የሚዋሹት? ከኔ ውጪ
ሊታዘብ የሚችል እነርሱ የሚያውቁት ዘመድ እንደሌላት ያውቃሉ። ምክንያቱም እንኳን የሰፈር ሰው እኔ ራሴ ዘመዶቿን
ያወቅኳቸው ስትሞት ነው። ራሳቸውን ነው የሚዋሹት? ይባስ ብለው እኔም እንድዋሻቸው ይፈልጋሉ፡፡ ረድኤት አባቷ ሲሞት እንዳደረገችው ጉድጓድ ውስጥ ካልገባሁ ብዬ እንድግደረደር
ይጠብቃሉ፡፡ ምን ብዬ ነው የማለቅስላት? ማን ይደብድበኝ? ማን ይስደበኝ? ማን ይርገመኝ? ብዬ? ስለእናቴ ሊመጣልኝ
የሚችለው ምስል ይሄ ብቻ ነው፡፡ ከራሷ ውጪ ማንንም አለመውደዷ፡፡
ከወለላ ሞት በኋላ “አባትህ ነኝ ብሎ አንድ ደልዳላ ሰው መጣ፡፡ወለላን ከፈታ በኋላ ሌላ ቤተሰብ መስርቶ ሶስት ልጆች
መውለዱን ነገረኝ፡፡ ብዙ የምጠይቀው ጥያቄ ቢኖርም አንዱን ብቻ መጠየቅ ቻልኩ።
“ወለላ አንተ ጥላኻት ከመሄድህ በፊት እንዴት ዓይነት ሴት ነበረች?”
“ባወቅካት መንገድ ብቻ እወቃት:: ላንተ እናትህ ናት። ለኔ ሚስቴ ነበረች፡፡ በየቱም መንገድ ወለላ እንደ እናትና እንደ
ሚስት አንድ አይነት ሴት ልትሆን አትችልም፡፡” አለኝ፡፡
“እጅግ እጠላታለሁ!” ያልኩት አስቤው አልነበረም፡፡ ድምፅ ማውጣቴ የገባኝ የእርሱን መደንገጥ ሳይ ነበር፡፡ ብዙ ነገር
የገባው መሰለኝ፡፡ መሰለኝ ብቻ!! ጥሎኝ ከቤት ሲወጣ ተከትዬው ወጣሁ።
“ወለላ እንዳረገዘችህ ሳውቅ ስምህን ቅዱስ ነበር ያልኩህ፡፡ ቅዱስ ጌታነህ” የአባቴን ስም ገና ዛሬ መስማቴ ነው፡፡ ይሄን ብሎኝ የአጥሩን በር ከፍቶ ወጣ፡፡ የእርሱን እግር ተክታ ረድኤት ገባች፡፡
“ማነው?” አለችኝ ።
“አባቴ!” ወደቤት እየገባሁ መለስኩላት፡፡ የምትናገረው ነገር የጠፋባት መሰለኝ፡፡ ሆኖ እንደማያውቀው ለደቂቃዎች ዝም
አለች።
ስሜ ቅዱስ ነበር። ቅዱስ ጌታነህ!" አልኳት። ሰውየው ስሜን ሲነግረኝ የተሰማኝ ስሜት የስም ለውጥ
የተነጠቅኩትን ማንነቴን መልሼ ያገኘሁ ዓይነት እንጂ!! ራሴን የሆንኩ አልመሰለኝም።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
#አዲስ_ዓመት
ፈጣሪ ከሞት ጠብቆ
ዕድሜ ሰጥቶናል መርቆ
ሰማይ ጥቁር ሰሌዳ
ከጉም ጠመኔ የጸዳ፣
ፀሓይ ፊቷን ገለጠች
ለዓለም ብርሃኗን ሰጠች፡፡
ከዋክብት ከጨረቃ ጋር
እንጸባርቂ በክብር፡፡
ማዕበል ዶፉ ጸጥ አለ
የወንዞች ሙላት ጎደላ፡፡
ምድር አሸበረቀች
በአበቦች ተንቆጠቆጠች፡፡
ጎመን ወጥቶ ከድስቱ
ገንፎው ገባ ምንቸቱ
ዕለታት ሒሳብ ሳይስቱ
መስከረም ጠባ በዓመቱ፡ ፡
ጨለማው ጠፍቶ በሀሓይ
ክረምት ተተካ በጸደይ፡፡
አዝርዕት ከሞት ተነሡ
ድርቀታቸውን ረሱ፡፡
በአበባ በፍሬ ደምቀው
ምግብን ሰጡ አሽተው፡፡
እንግዲህ እኛም ሕያዋን
እንመሳለሰ በብርሃን።
ሐሚት ቂምና ቁጣ
ጥላቻን ከልብ እናውጣ!
ክፋት የተንኮል ወጥመድ
ከዓለናችን ይወገድ”
የዝሙት የኃጢአት ጎመን
ከቤታችን ይውጣልን
ምግባር የእምነት ገንፎ
ከዘመን ዘመንን አልፎ
ለትውልድ ይቀመጥ ተርፎ
አምላክ ቅዱሰ መንፈስ
ሕይወታችንን ይቀድስ
ሥጋችንም በጽድቅ ይታደስ
መስከረም እዲሰ ዘመን
የሰላም የጤና እንዲሆን
ፈጣሪ ፈቃዱ ይሁን
አምላክ የፍቅር ጌታ
ዓመቱን ያድርግ የደስታ፡፡
🔘በኤፍሬም የኔሰው🔘
ፈጣሪ ከሞት ጠብቆ
ዕድሜ ሰጥቶናል መርቆ
ሰማይ ጥቁር ሰሌዳ
ከጉም ጠመኔ የጸዳ፣
ፀሓይ ፊቷን ገለጠች
ለዓለም ብርሃኗን ሰጠች፡፡
ከዋክብት ከጨረቃ ጋር
እንጸባርቂ በክብር፡፡
ማዕበል ዶፉ ጸጥ አለ
የወንዞች ሙላት ጎደላ፡፡
ምድር አሸበረቀች
በአበቦች ተንቆጠቆጠች፡፡
ጎመን ወጥቶ ከድስቱ
ገንፎው ገባ ምንቸቱ
ዕለታት ሒሳብ ሳይስቱ
መስከረም ጠባ በዓመቱ፡ ፡
ጨለማው ጠፍቶ በሀሓይ
ክረምት ተተካ በጸደይ፡፡
አዝርዕት ከሞት ተነሡ
ድርቀታቸውን ረሱ፡፡
በአበባ በፍሬ ደምቀው
ምግብን ሰጡ አሽተው፡፡
እንግዲህ እኛም ሕያዋን
እንመሳለሰ በብርሃን።
ሐሚት ቂምና ቁጣ
ጥላቻን ከልብ እናውጣ!
ክፋት የተንኮል ወጥመድ
ከዓለናችን ይወገድ”
የዝሙት የኃጢአት ጎመን
ከቤታችን ይውጣልን
ምግባር የእምነት ገንፎ
ከዘመን ዘመንን አልፎ
ለትውልድ ይቀመጥ ተርፎ
አምላክ ቅዱሰ መንፈስ
ሕይወታችንን ይቀድስ
ሥጋችንም በጽድቅ ይታደስ
መስከረም እዲሰ ዘመን
የሰላም የጤና እንዲሆን
ፈጣሪ ፈቃዱ ይሁን
አምላክ የፍቅር ጌታ
ዓመቱን ያድርግ የደስታ፡፡
🔘በኤፍሬም የኔሰው🔘
#ቀላውጦ_ማስመለስ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
የሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ መጀመርያው የማይታወቅ ክስተት እንኳን ቢሆን ቀጣይ አለው።ከመጀመርያው ወይ ካለፈው የሚያያይዘው አምድ የድር ያህል የቀጠነ ቢሆንም....ሁሌም ከማሃል ቆመህራስህን ስታገኘው መጀመርያውን የምትጠይቀው ለዛ ነው።
=========================
"ከኔና ከሱሶችህ ምረጥ" ስትለኝ ቀኑ ቅዳሜ ነበር።ስልኬን ጆሮዬ ላይ እንደለጠፍኩ ዙሪያዬን ቃኘሁት፡፡ በሱሶቼ ተከብቤያለሁ።(ያሟላሁ ሱሰኛ ነኝ፡፡)
"መቼ?" አልኳት።
"አሁኑኑ!"
"ዛሬ ከሆነ ሱሴን ነገ ከሆነ ግን አንቺን!” መለስኩላት፡፡ዘጋችው።መልሳ እንደማትደውል አውቃለሁ፡፡ ጥፋተኛው ማነው? ራሷን ከቅጠል ጋር፣ ከጭስ ጋር በሚዛን አስቀምጣልኝ ምን ልበላት?
ከባለቤቱ ያወቀ ቡዳ ነው' ዋጋዋን ከሷ በላይ እንዴት ላውቀው እችላለሁ? ስንተኛዬ እንደሆነች የማላስታውሳት ሴቴ ናት።ሴቶቼ እድሌ ሆኖ ነው መሰል ሱሴን ይጠምዱታል። እኔ ደሞ ፀባዬ ሆኖ ሱሰኛ ሴት ቅልሽልሽቴን ታመጣዋለች:: "በማን ላይ ተቀምጠህ ማንን ታማለህ?" ትለኛለች አለቃዬ(ስምረት) እኔ ስምሪት ነው የምላት አትናደድብኝም:: ከጠዋት ይልቅ ለለሊት የቀረበ ሰዓት ላይ ቢሮ ትገባና ተሰይማ ትጠብቀናለች:: ከጠዋት
ይልቅ ለከሰዓት በቀረበ ሰዓት ቢሮ እከስታለሁ፡፡
"እስቲ አንተን የማላባርርበት አንድ ጥሩ ምክንያት ብቻ ንገረኝ" ትለኛለች፡፡
"ያንቺ ደግነት!" እላታለሁ፡፡
"ወደ ስራ!" ብላ የመጨረሻውን ተሰማሪ ታሰማራኛለች ስምሪት።
ሴት ወዳለሁ። “ማን ይጠላል? አልክ የአዳም ዘር? ሃሃሃሃ..የምሬን እኮ ነው። እኔ ወዳቸዋለሁ። ሳስበው ፈጣሪ በምድር ላይ እንደ ሴት ውብና አማላይ አድርጎ ለፈተና የፈጠረው ነገር
መኖሩን እንጃ!! ገና ሳስባቸው ደም ስሬን የሚወጥሩ ፍጥረቶች ናቸው።ኤጭ አሁን ራሱ ደሜ ሞቀ! እነሱ ከሚወዱኝ የበዛ
ይናደዱብኛል!! "ሴት ሳይሆን ስሪያ ነው የምትወደው" ይሉኛል፡፡
“ስሪያው ታዲያ ከወንድ ጋር ነው እንዴ?" እላቸዋለሁ፡፡
በእርግጥ ከሴት ጋር ሱስ ስለማቆም ከማውራት 'አክሱሜን የሚያቆም ወሬ ማውራት እመርጣለሁ፡፡ (የኢትዮጵያን አክሱም እያልኩህ አይደለም።የራሴን አክሱም!) ሴትና ስሪያ ከመውደዴ
የተነሳ እንደውም ሳስበው መቃብሬ ላይ ራሱ አልቤርጎ ሚሰራ ነው የሚመስለኝ።
"አብረኸት ሆነህ የተለየ ደስ የሚል ስሜት የፈጠረችብህ ሴት የለችም?" ትለኛለች ስምሪት ስለሴቶቼ ስናወራ።
"አብሬያት ሆኜ የሚያስጠላ ስሜት የፈጠረችብኝን ሴት አላስታውስም::" እመልስላታለሁ:: እውነቴን ነው፡፡ በእርግጥ ረዥሙ ከሴት ጋር ቆይታዬ ሁለት ወር ነው። አንድም ቀን ያወቅኳትን ሴት ሁለት ወር ከማውቃት እኩል እወዳታለሁ። ስምሪት ደወለች::
"ወዬ?" መልስ የለም።
"ወዬ ስምሪት?" አልኩኝ ደግሜ፡፡ ከትንፋሽ ውጪ የሚሰማኝ ስላልነበር ዘጋሁትና መልሼ ደወልኩ፡፡ ይነሳል ግን መልስ የለም።
በነገራችሁ ላይ ስምሪት በኔ ውስጥ ፆታ አልባ ናት!! የሆነ ከማውቃቸው
ሴቶች የሚለያት እንደ ሴት እንዳላስባት
የሚያደርገኝ ነገር አላት፡፡ ምናልባት የምትለብሰው የፖሊስ ልብስ፣ ምናልባት ሁለት ሰዓት ለፍልፌባት በሁለት ደቂቃ
የምትመልስልኝ ልብ የሚያሳርፍ መልሷ፣ ምናልባት አለቃዬ መሆኗ፣ ምናልባትም ጆሮዬ እስኪጠነዛ ስለ ሴት መዋቢያና ማጌጫ ከሚያወሩኝ ሴቶች ስለምትለይ፣ ምናልባት የምትመርጣቸው ሮክ ሙዚቃዎችና የስለላ ፊልሞች ከብዙ ሴቶች ምርጫ መለየቱ ምናልባት....ምናልባት...በብዙ ምናልባቶች ፆታ አልባ ናት!! ወንድ ጓደኛ ሲኖረኝ ላወራው የምችለውን ቅሽምናዬን ሳወራት በከፊል ፈገግታ ከመስማት ውጪ አትፈረድብኝም።ስለፅድቅና ኀጢኣት አትሰብከኝም። የሚሰለቸኝ ስብከት መሆኑን ታውቃለች፡፡ ይሄ ማህበረሰብ ምኔ ነው? ምን የሰጠኝን ነው ሊቀበለኝ እጁን የሚዘረጋው? የእጁ አሻራ እስኪጠፋ ከሳሙና ጋር እንዳልተዳራ ከተለያየ ሴት ጋር መታየቴ ኀጢኣት መሆኑን ሊነግረኝ ይዳዳዋል፡፡ ያንተ ኀጢኣት የእኔን ኀጢኣት ፅድቅ
አያደርገውም፡፡ ቢሆንም ግን ራስህን በፃዲቅ ሂሳብ አስልተህ እኔን ለመኮነን ትክክለኛው ሜዳ ላይ አይደለህም:: በሀያ ዘጠኝ የእድሜዬ ቁጥር ላይ የተጓዙበት ይመስል የልክ መስመርን ሊያሰምሩልኝ እና ሊመክሩኝ ይፈልጋሉ:: ጥፋት መሆኑን
ሳላውቅ የማጠፋው ጥፋት አለ እና ነው? ችግሩ አንዳንዴ ልክ እንዳልሆነ በልብህ እያወቅክም ታደርገዋለህ።ብትፀፀትም ግን ትደግመዋለህ፡፡ ታዲያ ምኑን ነው የሚመክሩኝ? በዚህ ዘብራቃ ማህበረሰብ ውስጥ ኀጢኣትህን ኀጢአት የሚያደርገው ድርጊቱ ሳይሆን ያደረግከው ድርጊት በግልፅ መሆኑ ነው። ተደብቀህ ካደረግከው ፅድቅህ ይተረካል፡፡
ከስምሪት ጋር ሶስት ዓመት አብረን ሰርተናል፡፡ እሷ መርማሪ ፖሊስ መሆን ህልሟ ነው:: እኔስ? እኔ ደግሞ ቅዠቴ፡፡ እዩልኝ ይሄ ግራ የገባው የጦዘ የኑሮ ስሌት እና አስተዳደር አላሚና ቃዢን በአንድ ያስተዳድራል።ለሶስተኛ ጊዜ መልሼ ደወልኩ።በተኮላተፈ አንደበት እና በተሰባበሩ ፊደላት የመለሰችልኝ ህፃን
ናት። ቀጣጥዬ የተረዳሁት ደግሞ "ስምረት ሞተች” የሚለውን ንግግር ነው። ዘልዬ ብድግ አልኩ።ይሄኛውን ራሴን
አላውቀውም። በምንም ክስተት እንዲህ እደነግጣለሁ ብዬ አስቤ አላውቅም።
ከርቀት የማውቀው የስምሪት ቤት ለመድረስ ላዳ ታክሲ ያዝኩ፡፡ሆኜ እንደማላውቀው ታክሲ ውስጥ ቁጭ ብድግ ሰራሁ። ሮጬ ቤቱን ሳንኳኳ የከፈተችልኝ ቅድም በስልክ ያዋራችኝ ህፃን ናት።የኦቲዝም ተጠቂ መሆኗን ለመገንዘብ ከአንድ ዕይታ በላይ
አይጠይቅም፡፡ ዘልዬ እየገባሁ ምን መጠየቅ እንዳለብኝ ግራ ስጋባ
በእጂ ምልክት የሻወር ቤቱን አሳየችኝ፡፡ ክፍት ነው:: ስምሪት ወለሉ ላይ እርቃኗን ተዘርራለች:: እርቃኗን ለቄንጥ የተዘረረች
የሚመስል አነጣጠፍ ነው ወለሉ ላይ የተነጠፈችው።ትንፋሿ መኖሩን ካረጋገጥኩ በኋላ ከወለሉ ላይ ተሸክሜ መኝታ ቤቷ አልጋዋ ላይ አስተኛኋት። በደመነፍስ ማድረግ ያለብኝ የመሰለኝ
ቁምሳጥኑን ከፍቼ ያገኘሁትን ልብስ ማውጣት ነበር። በፎጣ ሰውነቷን አደራርቄ ሳበቃ ፓንቷን አለበስኳት:: የሴት ልጅ ፓንት ያወለቅኩበት ጊዜ እንጂ ያለበስኩበት ቀን አልከሰትልህ አለኝ። የሆነ ገለፃ አልባ ነገር እየተሰማኝ ልብሷን አለባበስኳት እና ወዳቆምኩት ታክሲ ተሸክሜያት ሄድኩ። ህፃኗ ድምፅ
የሌለው ለቅሶ እያለቀሰች እየተከተለችኝ እንደሆነ ያወቅኩት ታክሲ ውስጥ ከገባሁ በኋላ ነው:: ግራ ተጋባሁ:: ይዣት
ልሂድ? ህፃን ናት እንዴት ትቻት እሄዳለሁ? የቤቱን በር ዘግቼው ታክሲው ውስጥ አስገብቻት አብረን መጓዝ ጀመርን።
ስምሪት እግሮቼ ላይ ናት፡፡
"ስምሪት ምንሽ ናት?" ጠየቅኩ ከስምሪት ላይ ዓይኗን ለአፍታ ያልነቀለችውን ህፃን:: በአትኩሮት በጥያቄ አየችኝ፡፡ ፊቷ ተቆጣ።
"ስምረት ምንሽ ናት?" አስተካክዬ ደገምኩ።
አልመለሰችልኝም። ስምሪት ስለራሷ ነግራኝ የምታውቀው ነገር ካለ ማሰብ ጀመርኩ። መርማሪ ፖሊስ መሆን ህልሟ መሆኑን ብቻ! አስቤው አላውቅም:: ጠይቄያት አላውቅም።ስለእኔ
የማልነግራት የለም:: እንዴት ሆንክ? ያ ነገር እንዴት ሆነልህ ያሁኗ ቺክህ እንዴት ናት? ምን ሆነህ ነው ፊትህ ልክ አይደለም? ዓይንህ ቀልቷል ማታ አልተኛህም እንዴ? ማውራት ትፈልጋለህ? የመሳሰሉ ጥያቄዎች ትጠይቀኛለች፡፡ የጠየቀችኝን እመልስላታለሁ። አንዲትም ቀን አንቺስ? ብያት አላውቅም ፊቷ ጠቆረ? ቀላ? አይቼው አላውቅም። እንደመስታወት የሚያብረቀርቅ የፀዳ ቀይ ፊት እንዳላት እንኳን ያስተዋልኩት
ዛሬ ነው:: በእርግጥ ስትናደድ ጉንጫ ሲቀላ ደስ ትለኛለች
“እናቴ ናት" አለችኝ ህፃኗ መጠየቄን የምረሳበት ያህል
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
የሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ መጀመርያው የማይታወቅ ክስተት እንኳን ቢሆን ቀጣይ አለው።ከመጀመርያው ወይ ካለፈው የሚያያይዘው አምድ የድር ያህል የቀጠነ ቢሆንም....ሁሌም ከማሃል ቆመህራስህን ስታገኘው መጀመርያውን የምትጠይቀው ለዛ ነው።
=========================
"ከኔና ከሱሶችህ ምረጥ" ስትለኝ ቀኑ ቅዳሜ ነበር።ስልኬን ጆሮዬ ላይ እንደለጠፍኩ ዙሪያዬን ቃኘሁት፡፡ በሱሶቼ ተከብቤያለሁ።(ያሟላሁ ሱሰኛ ነኝ፡፡)
"መቼ?" አልኳት።
"አሁኑኑ!"
"ዛሬ ከሆነ ሱሴን ነገ ከሆነ ግን አንቺን!” መለስኩላት፡፡ዘጋችው።መልሳ እንደማትደውል አውቃለሁ፡፡ ጥፋተኛው ማነው? ራሷን ከቅጠል ጋር፣ ከጭስ ጋር በሚዛን አስቀምጣልኝ ምን ልበላት?
ከባለቤቱ ያወቀ ቡዳ ነው' ዋጋዋን ከሷ በላይ እንዴት ላውቀው እችላለሁ? ስንተኛዬ እንደሆነች የማላስታውሳት ሴቴ ናት።ሴቶቼ እድሌ ሆኖ ነው መሰል ሱሴን ይጠምዱታል። እኔ ደሞ ፀባዬ ሆኖ ሱሰኛ ሴት ቅልሽልሽቴን ታመጣዋለች:: "በማን ላይ ተቀምጠህ ማንን ታማለህ?" ትለኛለች አለቃዬ(ስምረት) እኔ ስምሪት ነው የምላት አትናደድብኝም:: ከጠዋት ይልቅ ለለሊት የቀረበ ሰዓት ላይ ቢሮ ትገባና ተሰይማ ትጠብቀናለች:: ከጠዋት
ይልቅ ለከሰዓት በቀረበ ሰዓት ቢሮ እከስታለሁ፡፡
"እስቲ አንተን የማላባርርበት አንድ ጥሩ ምክንያት ብቻ ንገረኝ" ትለኛለች፡፡
"ያንቺ ደግነት!" እላታለሁ፡፡
"ወደ ስራ!" ብላ የመጨረሻውን ተሰማሪ ታሰማራኛለች ስምሪት።
ሴት ወዳለሁ። “ማን ይጠላል? አልክ የአዳም ዘር? ሃሃሃሃ..የምሬን እኮ ነው። እኔ ወዳቸዋለሁ። ሳስበው ፈጣሪ በምድር ላይ እንደ ሴት ውብና አማላይ አድርጎ ለፈተና የፈጠረው ነገር
መኖሩን እንጃ!! ገና ሳስባቸው ደም ስሬን የሚወጥሩ ፍጥረቶች ናቸው።ኤጭ አሁን ራሱ ደሜ ሞቀ! እነሱ ከሚወዱኝ የበዛ
ይናደዱብኛል!! "ሴት ሳይሆን ስሪያ ነው የምትወደው" ይሉኛል፡፡
“ስሪያው ታዲያ ከወንድ ጋር ነው እንዴ?" እላቸዋለሁ፡፡
በእርግጥ ከሴት ጋር ሱስ ስለማቆም ከማውራት 'አክሱሜን የሚያቆም ወሬ ማውራት እመርጣለሁ፡፡ (የኢትዮጵያን አክሱም እያልኩህ አይደለም።የራሴን አክሱም!) ሴትና ስሪያ ከመውደዴ
የተነሳ እንደውም ሳስበው መቃብሬ ላይ ራሱ አልቤርጎ ሚሰራ ነው የሚመስለኝ።
"አብረኸት ሆነህ የተለየ ደስ የሚል ስሜት የፈጠረችብህ ሴት የለችም?" ትለኛለች ስምሪት ስለሴቶቼ ስናወራ።
"አብሬያት ሆኜ የሚያስጠላ ስሜት የፈጠረችብኝን ሴት አላስታውስም::" እመልስላታለሁ:: እውነቴን ነው፡፡ በእርግጥ ረዥሙ ከሴት ጋር ቆይታዬ ሁለት ወር ነው። አንድም ቀን ያወቅኳትን ሴት ሁለት ወር ከማውቃት እኩል እወዳታለሁ። ስምሪት ደወለች::
"ወዬ?" መልስ የለም።
"ወዬ ስምሪት?" አልኩኝ ደግሜ፡፡ ከትንፋሽ ውጪ የሚሰማኝ ስላልነበር ዘጋሁትና መልሼ ደወልኩ፡፡ ይነሳል ግን መልስ የለም።
በነገራችሁ ላይ ስምሪት በኔ ውስጥ ፆታ አልባ ናት!! የሆነ ከማውቃቸው
ሴቶች የሚለያት እንደ ሴት እንዳላስባት
የሚያደርገኝ ነገር አላት፡፡ ምናልባት የምትለብሰው የፖሊስ ልብስ፣ ምናልባት ሁለት ሰዓት ለፍልፌባት በሁለት ደቂቃ
የምትመልስልኝ ልብ የሚያሳርፍ መልሷ፣ ምናልባት አለቃዬ መሆኗ፣ ምናልባትም ጆሮዬ እስኪጠነዛ ስለ ሴት መዋቢያና ማጌጫ ከሚያወሩኝ ሴቶች ስለምትለይ፣ ምናልባት የምትመርጣቸው ሮክ ሙዚቃዎችና የስለላ ፊልሞች ከብዙ ሴቶች ምርጫ መለየቱ ምናልባት....ምናልባት...በብዙ ምናልባቶች ፆታ አልባ ናት!! ወንድ ጓደኛ ሲኖረኝ ላወራው የምችለውን ቅሽምናዬን ሳወራት በከፊል ፈገግታ ከመስማት ውጪ አትፈረድብኝም።ስለፅድቅና ኀጢኣት አትሰብከኝም። የሚሰለቸኝ ስብከት መሆኑን ታውቃለች፡፡ ይሄ ማህበረሰብ ምኔ ነው? ምን የሰጠኝን ነው ሊቀበለኝ እጁን የሚዘረጋው? የእጁ አሻራ እስኪጠፋ ከሳሙና ጋር እንዳልተዳራ ከተለያየ ሴት ጋር መታየቴ ኀጢኣት መሆኑን ሊነግረኝ ይዳዳዋል፡፡ ያንተ ኀጢኣት የእኔን ኀጢኣት ፅድቅ
አያደርገውም፡፡ ቢሆንም ግን ራስህን በፃዲቅ ሂሳብ አስልተህ እኔን ለመኮነን ትክክለኛው ሜዳ ላይ አይደለህም:: በሀያ ዘጠኝ የእድሜዬ ቁጥር ላይ የተጓዙበት ይመስል የልክ መስመርን ሊያሰምሩልኝ እና ሊመክሩኝ ይፈልጋሉ:: ጥፋት መሆኑን
ሳላውቅ የማጠፋው ጥፋት አለ እና ነው? ችግሩ አንዳንዴ ልክ እንዳልሆነ በልብህ እያወቅክም ታደርገዋለህ።ብትፀፀትም ግን ትደግመዋለህ፡፡ ታዲያ ምኑን ነው የሚመክሩኝ? በዚህ ዘብራቃ ማህበረሰብ ውስጥ ኀጢኣትህን ኀጢአት የሚያደርገው ድርጊቱ ሳይሆን ያደረግከው ድርጊት በግልፅ መሆኑ ነው። ተደብቀህ ካደረግከው ፅድቅህ ይተረካል፡፡
ከስምሪት ጋር ሶስት ዓመት አብረን ሰርተናል፡፡ እሷ መርማሪ ፖሊስ መሆን ህልሟ ነው:: እኔስ? እኔ ደግሞ ቅዠቴ፡፡ እዩልኝ ይሄ ግራ የገባው የጦዘ የኑሮ ስሌት እና አስተዳደር አላሚና ቃዢን በአንድ ያስተዳድራል።ለሶስተኛ ጊዜ መልሼ ደወልኩ።በተኮላተፈ አንደበት እና በተሰባበሩ ፊደላት የመለሰችልኝ ህፃን
ናት። ቀጣጥዬ የተረዳሁት ደግሞ "ስምረት ሞተች” የሚለውን ንግግር ነው። ዘልዬ ብድግ አልኩ።ይሄኛውን ራሴን
አላውቀውም። በምንም ክስተት እንዲህ እደነግጣለሁ ብዬ አስቤ አላውቅም።
ከርቀት የማውቀው የስምሪት ቤት ለመድረስ ላዳ ታክሲ ያዝኩ፡፡ሆኜ እንደማላውቀው ታክሲ ውስጥ ቁጭ ብድግ ሰራሁ። ሮጬ ቤቱን ሳንኳኳ የከፈተችልኝ ቅድም በስልክ ያዋራችኝ ህፃን ናት።የኦቲዝም ተጠቂ መሆኗን ለመገንዘብ ከአንድ ዕይታ በላይ
አይጠይቅም፡፡ ዘልዬ እየገባሁ ምን መጠየቅ እንዳለብኝ ግራ ስጋባ
በእጂ ምልክት የሻወር ቤቱን አሳየችኝ፡፡ ክፍት ነው:: ስምሪት ወለሉ ላይ እርቃኗን ተዘርራለች:: እርቃኗን ለቄንጥ የተዘረረች
የሚመስል አነጣጠፍ ነው ወለሉ ላይ የተነጠፈችው።ትንፋሿ መኖሩን ካረጋገጥኩ በኋላ ከወለሉ ላይ ተሸክሜ መኝታ ቤቷ አልጋዋ ላይ አስተኛኋት። በደመነፍስ ማድረግ ያለብኝ የመሰለኝ
ቁምሳጥኑን ከፍቼ ያገኘሁትን ልብስ ማውጣት ነበር። በፎጣ ሰውነቷን አደራርቄ ሳበቃ ፓንቷን አለበስኳት:: የሴት ልጅ ፓንት ያወለቅኩበት ጊዜ እንጂ ያለበስኩበት ቀን አልከሰትልህ አለኝ። የሆነ ገለፃ አልባ ነገር እየተሰማኝ ልብሷን አለባበስኳት እና ወዳቆምኩት ታክሲ ተሸክሜያት ሄድኩ። ህፃኗ ድምፅ
የሌለው ለቅሶ እያለቀሰች እየተከተለችኝ እንደሆነ ያወቅኩት ታክሲ ውስጥ ከገባሁ በኋላ ነው:: ግራ ተጋባሁ:: ይዣት
ልሂድ? ህፃን ናት እንዴት ትቻት እሄዳለሁ? የቤቱን በር ዘግቼው ታክሲው ውስጥ አስገብቻት አብረን መጓዝ ጀመርን።
ስምሪት እግሮቼ ላይ ናት፡፡
"ስምሪት ምንሽ ናት?" ጠየቅኩ ከስምሪት ላይ ዓይኗን ለአፍታ ያልነቀለችውን ህፃን:: በአትኩሮት በጥያቄ አየችኝ፡፡ ፊቷ ተቆጣ።
"ስምረት ምንሽ ናት?" አስተካክዬ ደገምኩ።
አልመለሰችልኝም። ስምሪት ስለራሷ ነግራኝ የምታውቀው ነገር ካለ ማሰብ ጀመርኩ። መርማሪ ፖሊስ መሆን ህልሟ መሆኑን ብቻ! አስቤው አላውቅም:: ጠይቄያት አላውቅም።ስለእኔ
የማልነግራት የለም:: እንዴት ሆንክ? ያ ነገር እንዴት ሆነልህ ያሁኗ ቺክህ እንዴት ናት? ምን ሆነህ ነው ፊትህ ልክ አይደለም? ዓይንህ ቀልቷል ማታ አልተኛህም እንዴ? ማውራት ትፈልጋለህ? የመሳሰሉ ጥያቄዎች ትጠይቀኛለች፡፡ የጠየቀችኝን እመልስላታለሁ። አንዲትም ቀን አንቺስ? ብያት አላውቅም ፊቷ ጠቆረ? ቀላ? አይቼው አላውቅም። እንደመስታወት የሚያብረቀርቅ የፀዳ ቀይ ፊት እንዳላት እንኳን ያስተዋልኩት
ዛሬ ነው:: በእርግጥ ስትናደድ ጉንጫ ሲቀላ ደስ ትለኛለች
“እናቴ ናት" አለችኝ ህፃኗ መጠየቄን የምረሳበት ያህል
👍1
የጊዜ እርዝመት ቆይታ።ልጅ እንዳላት ስታወራ ሰምቼ አላውቅም።እንዴት አትነግረኝም? ለምን ትነግረኛለች? መች እንድትነግረኝ
ጠየቅኳት? ምናልባት ልትነግረኝ አስባ ታውቅ ይሆናል። እኔ ግድ እንደሌለኝ ታውቃለች። ጆሮውን እንኳን ሊያውሳት ቁብ ላልሰጠው ሰው ለምን ትነግረኛለች? እሷ ታዲያ ለምን ትሰማኛለች? ለምን ትጠይቀኛለች? ለምን ውሎ አዳሬ ያሳስባታል?
“እናቴ ናት” ደገመችልኝ ህፃኗ ትኩረት የሰጠኋት አልመሰላትም።
"ስምሽ ማነው?" አልኳት።
“
"አርሴማ"
ስምሪት ነቅታ ተንቀሳቀሰች። ዓይኖቿ ስትገልጣቸው ድልህ መስለዋል። በመጠኑ እፎይታ ተሰማኝ:: አርሴማ መንቃቷን ስታውቅ ቦረቀች::
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
ጠየቅኳት? ምናልባት ልትነግረኝ አስባ ታውቅ ይሆናል። እኔ ግድ እንደሌለኝ ታውቃለች። ጆሮውን እንኳን ሊያውሳት ቁብ ላልሰጠው ሰው ለምን ትነግረኛለች? እሷ ታዲያ ለምን ትሰማኛለች? ለምን ትጠይቀኛለች? ለምን ውሎ አዳሬ ያሳስባታል?
“እናቴ ናት” ደገመችልኝ ህፃኗ ትኩረት የሰጠኋት አልመሰላትም።
"ስምሽ ማነው?" አልኳት።
“
"አርሴማ"
ስምሪት ነቅታ ተንቀሳቀሰች። ዓይኖቿ ስትገልጣቸው ድልህ መስለዋል። በመጠኑ እፎይታ ተሰማኝ:: አርሴማ መንቃቷን ስታውቅ ቦረቀች::
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
❤1
#የጥቅምት_መስክ_ነኝ!!
ሰው ለሰው ይፈርዳል
ልብን ዘልቆ ሳያይ
ላልቃሽ እያዘነ
በፈካ ገጽ ውስጥ፣ ያደፈጠን ሥቃይ
ማነው የመዘነ?
የይስሙላም ይሁን፤ ከልብ ያለቀሰ
አያጣም አይዞህ ባይ
ካንጀት ይሁን ካንገት፣ እንባ ላፈሰሰ
አይጠፋም ከመንገድ፣ መሐረብ አቀባይ።
ይብላኝ ላሳሳች ፊት፣ አፅናኝ ለማይጋብዝ
አንዳንድ ሀዘን አለ
ከላይ ተሰውሮ፣ ልብ የሚበዘብዝ
የጥቅምት ብሩህ መስክ፣ አደይ የለበሰ
ስንቱን ጉድ አዝሎታል፣ ሥሩ ከተማሰ!!
የጥቅምት መስክ ነኝ፣ አደይ ያደመቀው
ፈገግታ ቢውጠው፣ ዘበት ቢደብቀው
የኔን ብቻ ሕመም፣ እኔው ነኝ የማውቀው።
🔘በእውቀቱ ስዩም🔘
ሰው ለሰው ይፈርዳል
ልብን ዘልቆ ሳያይ
ላልቃሽ እያዘነ
በፈካ ገጽ ውስጥ፣ ያደፈጠን ሥቃይ
ማነው የመዘነ?
የይስሙላም ይሁን፤ ከልብ ያለቀሰ
አያጣም አይዞህ ባይ
ካንጀት ይሁን ካንገት፣ እንባ ላፈሰሰ
አይጠፋም ከመንገድ፣ መሐረብ አቀባይ።
ይብላኝ ላሳሳች ፊት፣ አፅናኝ ለማይጋብዝ
አንዳንድ ሀዘን አለ
ከላይ ተሰውሮ፣ ልብ የሚበዘብዝ
የጥቅምት ብሩህ መስክ፣ አደይ የለበሰ
ስንቱን ጉድ አዝሎታል፣ ሥሩ ከተማሰ!!
የጥቅምት መስክ ነኝ፣ አደይ ያደመቀው
ፈገግታ ቢውጠው፣ ዘበት ቢደብቀው
የኔን ብቻ ሕመም፣ እኔው ነኝ የማውቀው።
🔘በእውቀቱ ስዩም🔘
👍1
#ቀላውጦ_ማስመለስ
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
ውድ አንባብያን ምንም የተቀየረ ድርሰት የለም እስካሁን የቀረቡትም በቀጣይም የሚቀርበውም #የቀላውጦ_ማስመለስ ተከታይ ክፍሎች ናቸው ነገር ግን ሃሳቦች በሙሉ ላያልቁ ይችላሉ እነዲዚ ሲያጋጥም በራሳችሁ እየጨረሳቹ አንዳንድ ታሪኮች ደሪሲው ብቻ አይጨርሳቸውም አመሰግናለው።
=========================
ስምሪት ነቅታ ተንቀሳቀሰች። ዓይኖቿ ስትገልጣቸው ድልህ መስለዋል። በመጠኑ እፎይታ ተሰማኝ። አርሴማ መንቃቷን ስታውቅ ቦረቀች::
"ወደ ቤት መልሰኝ ምንም አልሆንም አንዳንዴ እንዲህ ያደርገኛል" አለችኝ የሆነውን ከነገርኳት በኋላ፡፡
"አንዳንዴ? መታየት አለብሽ?"
“እንቅልፍ ተኚ፣ እረፍት አድርጊ፣ ፈሳሽ ውስጂ” ነው የሚሉኝ" አለች ከእግሮቼ ላይ ለመነሳት እየተነቃቃች። ብዙ
በእንቢታዋ ፀናች፡፡ ሀሳቧን እንድትቀይር
እየነተረኳት ወደ ቤት ተመለስን፡፡ ምንም የማውራት ፍላጎት አልነበረኝም፡፡ እሷም እቤቷ መቀመጤ ምቾት የሰጣት
አይመስለኝም፡፡ አርሴማ እናቷ ጉያ ተሸጉጣ ቁልጭ ቁልጭ እያለች አንዴ እኔን አንዴ እናቷን ታያለች።
"ደህና ትሆኛለሽ? ልሂድ?" አልኳት፡፡
"አዎን ደህና እሆናለሁ ሂድ!" አለችኝ የመገላገል አይነት ስሜት ባለው ድምፅ።
ከቤቷ ወጥቼ በእግሬ ብዙ መንገድ እየተጓዝኩ ጭንቅላቴ ስለስምሪት የግርታ ቁልል መደርመሱን አላቆመም:: (ይህቺ ሴት ማናት? አላውቃትም ነበር ማለት ነው? ወይም የፖሊስ ልብሷን ስታወልቅ ቁሌታም ትሆናለች?) እንዲህ የማስበው መታጠቢያ ቤቷ ውስጥ ተዘርራ ያየሁት ሰውነቷ አንድ በአንድ ሲታወሰኝ
ነው። መሬቱ ላይ ተዘርራ አልፎ አልፎ የሳሙና አረፋ ሰውነቷ ላይ መኖሩ ሸራ ላይ የተሳለች ስዕል አስመስሏት ነበር። ከፊል ፀጉሯ ወለሉ ላይ ተበትኗል፡፡ ከፊሉ በትከሻዋ አልፎ ደረቷንና የግራ ጡቷን ሸፍኖታል፡፡ (ፀጉሯን ሁሌም ጠቅልላ ነው
የማውቃት ረዥም ፀጉር እንዳላት አስቤ አላውቅም፡፡ ኸረ ፀጉር እንዳላትም ትኩረት ሰጥቼ አይቻት አላውቅም።) የቀኝ እጇ የቀኝ ጡቷን በከፊል ከልሎ ዘንፈል ብሏል፡፡ ጡቶቿ በአንድ ጨረፍታ እይታ ብቻ በጭንቅላት ውስጥ ይሳላሉ፡፡ የግራ እጇ ወለሉ ላይ ተጥሏል።ከጀርባዋ የተጣበቀው ሆዷ እና ከታችኛው አካሏ ጋር ሲተያይ የሌላ ቀጭን ሴት የሚመስል የሰመጠ ወገቧ በአንድ ጎኗ ወለሉን ተደግፈዋል፡፡ እግሮቿ በመጠኑ ገርበብ ብለው ቀኙ አጠፍ ብሎ ግራው ተዘርግቷል። አይቼ አለመገረም ያቃተኝ
ዙሪያውን ተላጭታው ለ'እሙሙዬዋ" የቀረበ ቦታ ላይ ትንሽዬ ሶስት ማዕዘን ቅርፅ የተወችለት ጭገሯ ነው፡፡ ይህቺን ሴት በፍፁም አላውቃትም።
ራሴን ፣እሷን፣ ልጇን፣ እየዛቆሉ የሚኖሩትን ይህ በስባሳ ኑሮ እያሰብኩ ሳይታወቀኝ ብዙ ተጓዝኩ፡፡ረበሸኝ፡፡ ግድ የለኝም፣ ረስቼዋለሁ፣ ተሻግሬዋለሁ ትላንት ልቤን እየጨመደደ ሲፈነቅለኝ ይታወቀኛል። ደጋግሜ አጨስኩ።ራስ ምታት ጀመረኝ፡፡
ያለፈው በሚመጣው ላይ ምንም ጥቀርሻ መተው የለበትም ብዬ ያለፈውን ከኔ አርቄ የጣልኩ ይመስለኝ ነበር፡፡ ምናልባት አይቻል ይሆናል፡፡ ዛሬ ከተከሰተው ክስተት ምኑ ከኔጋ እንደሚያያዝ አላውቅም።የሰው
ልጅ ሁሉ ከትላንቱ ተጋብቶ ሳይሆን
አይቀርም የሚኖረው። ዛሬው የትላንት ጭማቂ ነዋ!! የዛሬ ግቡ የትናንት ምክንያቱ ነበራ! ከዓመታት በፊት እናቴ ወይ አባቴ ያነቡት እንባ ምክንያቱን እንኳን ሳይቀይር በልጃቸው ጉንጭ
ላይ ሊወርድ ይችላል፡፡ አባቶች በበሉት መራር ፍሬ የልጆች ጥርስ በለዘ አይነት ሆኖብኝ ትላንት ትዝታ ብቻ አለመሆኑ
የገባኝ ዛሬ ነው፡፡ ትናንት ትውልድን እንኳን ጥሶ እንደሚያልፍ አስቤ አላውቅም ነበር፡፡ ሀበሻ ሙዚቃው ውስጥ እንኳን ትዝታ ስልት መኖሩ ከትናንት መፋታት አለመፈለጉ ወይ አለመቻሉ ይሆናል፡፡ ስልኬ ጮኸ፡ ስምሪት ናት። ደነገጥኩ።
"ወዬ ምነው? አመመሽ እንዴ?"
“ኸረ ደህና ነኝ። ቅድም ስላልተረጋጋሁ አመሰግናለሁ እንኳን ሳልልህ!”
“አሁን አልሺኝ!" ብያት ስልኬን ዘጋሁት:: ከትናንትናዬ መዘጋጋት ግን አቃተኝ።
እናቴ ሸርሙጣ ነበረች፡፡ ሀገር ያወቃት ሽርሙጣ፡፡ ስለእርሷ ሲወራ የምሰማው የባሎቿን ብዛት እና የወንዶቿን መደራረብ
ነበር፡፡ እኔን እንኳን ከማን እንደወለደችኝ አታውቅም:: ባሏ ነው የሷ ዲቃላ መሆኔን የሚነግረኝ፡፡ እሷም ጋንጩራ የሰፈረባት
ቀን ሂድ ከዚህ ጥፋ! ዲቃላ ትለኛለች ስትሰድበኝ የሌላ ሰው ነውር እንደሆንኩ ሁላ... እናቴ ምንም አትገባኝም:
አንዳንዴ አቅፋኝ ስቅስቅ ብላ ታለቅሳለች፡፡ ወዲያው መልሳ ለዓይኗ እቀፋትና ዞር በልልኝ ትለኛለች፡፡ ቆንጆ ናት።ህልም የመሰለች ቆንጆ! ባሏ ደግሞ ጥንቅቅ ያለ ሱሰኛ ነው:: እናቴንና ባሏን በተመለከተ ብዙ ያልጠየቅኳቸው ያልተመለሱልኝ
ጥያቄዎች አሉ። ማወቅም አለማወቅም የሚሰጠኝ ሽራፊ ስሜት አልነበረም፡፡ እናቴ እንዴት አንድ ዘመድ እንኳን አይኖራትም? አላውቅም! የምንኖርበትን ቪላ አወረሱኝ የምትላቸው ቤተቦቿ
እንዴት አንዲት የዘር ትራፊ አይኖራቸውም? ለምን በየቀኑ
ከተለያየ ወንድ ጋር ትሆናለች? ሲያሻት ራሱ ጠባቂ ለሚያስፈልገው ባሏ ትታኝ የት ነው ከርማ የምትመጣው? ባሏስ
ከመስከር ውጪ የሚያደርገው የመልስ
ምት እንዴት አይኖርም? አላውቅም። እነሱ ለኔ ግድ እንደሌላቸው ሁሉ እኔም
ጉድጓድ ቢገቡ ግድ አልነበረኝም፡፡ አብራን በምትሆንባቸው ምሽቶች እሱ ሰክሮ ይገባል። እሷ ተኳኩላ ትወጣለች፡፡ ለቀናት ጥላን የምትጠፋበት ጊዜም የእድሜዬ ግማሽ ያህል ነው።
ለዓመታት ያልነበረችበት ዘመንም ነበረ። የስምንት ዓመት ልጅ ስሆን ጥላን ሄደች:: የት መሆኑን ባሏም አያውቅም፡፡ ከሁለት ዓመት በኋላ ስትመለስም የማንንም ጥያቄ ያለመመለስ መብትና እብሪት ነበራት። የሚቀጥለውን አራት ዓመት አብራን ስሆን ብቅ ጥልቅ ማለቷ ቀርቶ ለባሏ ጥላኝ ሄደች።እሷ ኖረችም
ሄደች ለውጡ ምንም ነው። ልጥገብ ወይ ልራብ፣ ልደስተ ወይ ልዘን፣ ልክሳ ወይ ልወፍር፣ ልማር ወይ ሜዳ ልዋል፣
ልታመም ወይ ጤነኛ ልሁን ሁለቱም ግዳቸው አይደለሁም ምናቸውም አልነበርኩም። አብሬያቸው ሆኜ የረሱኝ ይመስላሉ።
በእርግጥ በፍቅር ከመደኅየታችን ውጪ በኑሮ የጎደለ ሽንቁር አላስታውስም።እሷ በማትኖርበት ጊዜም ከምንኖርበት ትልቁ ቤት ጀርባ የሚከራዩ ሰርቪስ ቤቶች በየወሩ ገቢ ስለነበረን አንቸገርም ነበር።
“እናትህ ሸርሙጣ ናት! ወንድ አትጠግብም።ለገንዘብ ብላ አይደለም የምትሸረሙጠው ሽርሙጥና ሱስ ሆኖባት ነው።ይለኛል ባሏ ይዞ ከመጣው ቢራ እየቀዳልኝ:: ጠዋት ግን ገንዘብ
ስትሰጠው አየዋለሁ።ከርሱ ጋር በየቀኑ እየሰከርኩ ማደር ልምዱ ነበር። ይቀዳልኛል፣ ይቀደድልኛል፣ ቀደዳውንም
ቢራውንም እጋታለሁ። አጣጩ እንጂ የማድግ ልጁ አይደለሁምና በየቀኑ የሚግተኝ አልኮል ምን እንደሚጎትትብኝ
ግድ አልነበረውም።እንደባል የሚጫወተው ምንም ካለመኖሩ
የተነሳ ለማመን ምንም ታክል የማይቀረኝን ሀሜት ስለእርሱ
ሳድግ ሰምቻለሁ። እናቴን ያገባት ትሰራ ከነበረችበት ሽርሙጥናዋ አስትቷት እንደነበር እራሱም ሲያወራ ሰምቻለሁ።
ሆቴል ስትሰራ ደንበኛዋ ከነበረ ሰው ጋር በትገባኛለች ፀብ አክሱሙ ከጥቅም ውጪ መሆኑን ሲያሙት በተደጋጋሚ
ሰምቻለሁ። ለወጉ በዓመቱ መጀመሪያ እንድታስመዘግበኝ ተለማምጫት ወይም እርሱን ለምኜው ት/ቤት እገባለሁ።
ዓመቱን ሙሉ እመላለሳለሁ፡፡ ስንተኛ ክፍል እንደሆንኩ አያውቁም። እድሜዬንም ይዘነጉታል። የትምህርት ቤት ስሜን ሁሉ የማስታውሳቸው እኔ ነኝ። የአባቴ ስም የባሏ ስም ነው።
"የማንም ዲቃላ አባት አይደለሁም:: አባትህን ሄደህ ፈልግ::"ይለኛል ከሷ ጋር ሲጣላ፡፡ እኔ ለነሱ የለሁም
፡
፡
#ክፍል_አምስት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
ውድ አንባብያን ምንም የተቀየረ ድርሰት የለም እስካሁን የቀረቡትም በቀጣይም የሚቀርበውም #የቀላውጦ_ማስመለስ ተከታይ ክፍሎች ናቸው ነገር ግን ሃሳቦች በሙሉ ላያልቁ ይችላሉ እነዲዚ ሲያጋጥም በራሳችሁ እየጨረሳቹ አንዳንድ ታሪኮች ደሪሲው ብቻ አይጨርሳቸውም አመሰግናለው።
=========================
ስምሪት ነቅታ ተንቀሳቀሰች። ዓይኖቿ ስትገልጣቸው ድልህ መስለዋል። በመጠኑ እፎይታ ተሰማኝ። አርሴማ መንቃቷን ስታውቅ ቦረቀች::
"ወደ ቤት መልሰኝ ምንም አልሆንም አንዳንዴ እንዲህ ያደርገኛል" አለችኝ የሆነውን ከነገርኳት በኋላ፡፡
"አንዳንዴ? መታየት አለብሽ?"
“እንቅልፍ ተኚ፣ እረፍት አድርጊ፣ ፈሳሽ ውስጂ” ነው የሚሉኝ" አለች ከእግሮቼ ላይ ለመነሳት እየተነቃቃች። ብዙ
በእንቢታዋ ፀናች፡፡ ሀሳቧን እንድትቀይር
እየነተረኳት ወደ ቤት ተመለስን፡፡ ምንም የማውራት ፍላጎት አልነበረኝም፡፡ እሷም እቤቷ መቀመጤ ምቾት የሰጣት
አይመስለኝም፡፡ አርሴማ እናቷ ጉያ ተሸጉጣ ቁልጭ ቁልጭ እያለች አንዴ እኔን አንዴ እናቷን ታያለች።
"ደህና ትሆኛለሽ? ልሂድ?" አልኳት፡፡
"አዎን ደህና እሆናለሁ ሂድ!" አለችኝ የመገላገል አይነት ስሜት ባለው ድምፅ።
ከቤቷ ወጥቼ በእግሬ ብዙ መንገድ እየተጓዝኩ ጭንቅላቴ ስለስምሪት የግርታ ቁልል መደርመሱን አላቆመም:: (ይህቺ ሴት ማናት? አላውቃትም ነበር ማለት ነው? ወይም የፖሊስ ልብሷን ስታወልቅ ቁሌታም ትሆናለች?) እንዲህ የማስበው መታጠቢያ ቤቷ ውስጥ ተዘርራ ያየሁት ሰውነቷ አንድ በአንድ ሲታወሰኝ
ነው። መሬቱ ላይ ተዘርራ አልፎ አልፎ የሳሙና አረፋ ሰውነቷ ላይ መኖሩ ሸራ ላይ የተሳለች ስዕል አስመስሏት ነበር። ከፊል ፀጉሯ ወለሉ ላይ ተበትኗል፡፡ ከፊሉ በትከሻዋ አልፎ ደረቷንና የግራ ጡቷን ሸፍኖታል፡፡ (ፀጉሯን ሁሌም ጠቅልላ ነው
የማውቃት ረዥም ፀጉር እንዳላት አስቤ አላውቅም፡፡ ኸረ ፀጉር እንዳላትም ትኩረት ሰጥቼ አይቻት አላውቅም።) የቀኝ እጇ የቀኝ ጡቷን በከፊል ከልሎ ዘንፈል ብሏል፡፡ ጡቶቿ በአንድ ጨረፍታ እይታ ብቻ በጭንቅላት ውስጥ ይሳላሉ፡፡ የግራ እጇ ወለሉ ላይ ተጥሏል።ከጀርባዋ የተጣበቀው ሆዷ እና ከታችኛው አካሏ ጋር ሲተያይ የሌላ ቀጭን ሴት የሚመስል የሰመጠ ወገቧ በአንድ ጎኗ ወለሉን ተደግፈዋል፡፡ እግሮቿ በመጠኑ ገርበብ ብለው ቀኙ አጠፍ ብሎ ግራው ተዘርግቷል። አይቼ አለመገረም ያቃተኝ
ዙሪያውን ተላጭታው ለ'እሙሙዬዋ" የቀረበ ቦታ ላይ ትንሽዬ ሶስት ማዕዘን ቅርፅ የተወችለት ጭገሯ ነው፡፡ ይህቺን ሴት በፍፁም አላውቃትም።
ራሴን ፣እሷን፣ ልጇን፣ እየዛቆሉ የሚኖሩትን ይህ በስባሳ ኑሮ እያሰብኩ ሳይታወቀኝ ብዙ ተጓዝኩ፡፡ረበሸኝ፡፡ ግድ የለኝም፣ ረስቼዋለሁ፣ ተሻግሬዋለሁ ትላንት ልቤን እየጨመደደ ሲፈነቅለኝ ይታወቀኛል። ደጋግሜ አጨስኩ።ራስ ምታት ጀመረኝ፡፡
ያለፈው በሚመጣው ላይ ምንም ጥቀርሻ መተው የለበትም ብዬ ያለፈውን ከኔ አርቄ የጣልኩ ይመስለኝ ነበር፡፡ ምናልባት አይቻል ይሆናል፡፡ ዛሬ ከተከሰተው ክስተት ምኑ ከኔጋ እንደሚያያዝ አላውቅም።የሰው
ልጅ ሁሉ ከትላንቱ ተጋብቶ ሳይሆን
አይቀርም የሚኖረው። ዛሬው የትላንት ጭማቂ ነዋ!! የዛሬ ግቡ የትናንት ምክንያቱ ነበራ! ከዓመታት በፊት እናቴ ወይ አባቴ ያነቡት እንባ ምክንያቱን እንኳን ሳይቀይር በልጃቸው ጉንጭ
ላይ ሊወርድ ይችላል፡፡ አባቶች በበሉት መራር ፍሬ የልጆች ጥርስ በለዘ አይነት ሆኖብኝ ትላንት ትዝታ ብቻ አለመሆኑ
የገባኝ ዛሬ ነው፡፡ ትናንት ትውልድን እንኳን ጥሶ እንደሚያልፍ አስቤ አላውቅም ነበር፡፡ ሀበሻ ሙዚቃው ውስጥ እንኳን ትዝታ ስልት መኖሩ ከትናንት መፋታት አለመፈለጉ ወይ አለመቻሉ ይሆናል፡፡ ስልኬ ጮኸ፡ ስምሪት ናት። ደነገጥኩ።
"ወዬ ምነው? አመመሽ እንዴ?"
“ኸረ ደህና ነኝ። ቅድም ስላልተረጋጋሁ አመሰግናለሁ እንኳን ሳልልህ!”
“አሁን አልሺኝ!" ብያት ስልኬን ዘጋሁት:: ከትናንትናዬ መዘጋጋት ግን አቃተኝ።
እናቴ ሸርሙጣ ነበረች፡፡ ሀገር ያወቃት ሽርሙጣ፡፡ ስለእርሷ ሲወራ የምሰማው የባሎቿን ብዛት እና የወንዶቿን መደራረብ
ነበር፡፡ እኔን እንኳን ከማን እንደወለደችኝ አታውቅም:: ባሏ ነው የሷ ዲቃላ መሆኔን የሚነግረኝ፡፡ እሷም ጋንጩራ የሰፈረባት
ቀን ሂድ ከዚህ ጥፋ! ዲቃላ ትለኛለች ስትሰድበኝ የሌላ ሰው ነውር እንደሆንኩ ሁላ... እናቴ ምንም አትገባኝም:
አንዳንዴ አቅፋኝ ስቅስቅ ብላ ታለቅሳለች፡፡ ወዲያው መልሳ ለዓይኗ እቀፋትና ዞር በልልኝ ትለኛለች፡፡ ቆንጆ ናት።ህልም የመሰለች ቆንጆ! ባሏ ደግሞ ጥንቅቅ ያለ ሱሰኛ ነው:: እናቴንና ባሏን በተመለከተ ብዙ ያልጠየቅኳቸው ያልተመለሱልኝ
ጥያቄዎች አሉ። ማወቅም አለማወቅም የሚሰጠኝ ሽራፊ ስሜት አልነበረም፡፡ እናቴ እንዴት አንድ ዘመድ እንኳን አይኖራትም? አላውቅም! የምንኖርበትን ቪላ አወረሱኝ የምትላቸው ቤተቦቿ
እንዴት አንዲት የዘር ትራፊ አይኖራቸውም? ለምን በየቀኑ
ከተለያየ ወንድ ጋር ትሆናለች? ሲያሻት ራሱ ጠባቂ ለሚያስፈልገው ባሏ ትታኝ የት ነው ከርማ የምትመጣው? ባሏስ
ከመስከር ውጪ የሚያደርገው የመልስ
ምት እንዴት አይኖርም? አላውቅም። እነሱ ለኔ ግድ እንደሌላቸው ሁሉ እኔም
ጉድጓድ ቢገቡ ግድ አልነበረኝም፡፡ አብራን በምትሆንባቸው ምሽቶች እሱ ሰክሮ ይገባል። እሷ ተኳኩላ ትወጣለች፡፡ ለቀናት ጥላን የምትጠፋበት ጊዜም የእድሜዬ ግማሽ ያህል ነው።
ለዓመታት ያልነበረችበት ዘመንም ነበረ። የስምንት ዓመት ልጅ ስሆን ጥላን ሄደች:: የት መሆኑን ባሏም አያውቅም፡፡ ከሁለት ዓመት በኋላ ስትመለስም የማንንም ጥያቄ ያለመመለስ መብትና እብሪት ነበራት። የሚቀጥለውን አራት ዓመት አብራን ስሆን ብቅ ጥልቅ ማለቷ ቀርቶ ለባሏ ጥላኝ ሄደች።እሷ ኖረችም
ሄደች ለውጡ ምንም ነው። ልጥገብ ወይ ልራብ፣ ልደስተ ወይ ልዘን፣ ልክሳ ወይ ልወፍር፣ ልማር ወይ ሜዳ ልዋል፣
ልታመም ወይ ጤነኛ ልሁን ሁለቱም ግዳቸው አይደለሁም ምናቸውም አልነበርኩም። አብሬያቸው ሆኜ የረሱኝ ይመስላሉ።
በእርግጥ በፍቅር ከመደኅየታችን ውጪ በኑሮ የጎደለ ሽንቁር አላስታውስም።እሷ በማትኖርበት ጊዜም ከምንኖርበት ትልቁ ቤት ጀርባ የሚከራዩ ሰርቪስ ቤቶች በየወሩ ገቢ ስለነበረን አንቸገርም ነበር።
“እናትህ ሸርሙጣ ናት! ወንድ አትጠግብም።ለገንዘብ ብላ አይደለም የምትሸረሙጠው ሽርሙጥና ሱስ ሆኖባት ነው።ይለኛል ባሏ ይዞ ከመጣው ቢራ እየቀዳልኝ:: ጠዋት ግን ገንዘብ
ስትሰጠው አየዋለሁ።ከርሱ ጋር በየቀኑ እየሰከርኩ ማደር ልምዱ ነበር። ይቀዳልኛል፣ ይቀደድልኛል፣ ቀደዳውንም
ቢራውንም እጋታለሁ። አጣጩ እንጂ የማድግ ልጁ አይደለሁምና በየቀኑ የሚግተኝ አልኮል ምን እንደሚጎትትብኝ
ግድ አልነበረውም።እንደባል የሚጫወተው ምንም ካለመኖሩ
የተነሳ ለማመን ምንም ታክል የማይቀረኝን ሀሜት ስለእርሱ
ሳድግ ሰምቻለሁ። እናቴን ያገባት ትሰራ ከነበረችበት ሽርሙጥናዋ አስትቷት እንደነበር እራሱም ሲያወራ ሰምቻለሁ።
ሆቴል ስትሰራ ደንበኛዋ ከነበረ ሰው ጋር በትገባኛለች ፀብ አክሱሙ ከጥቅም ውጪ መሆኑን ሲያሙት በተደጋጋሚ
ሰምቻለሁ። ለወጉ በዓመቱ መጀመሪያ እንድታስመዘግበኝ ተለማምጫት ወይም እርሱን ለምኜው ት/ቤት እገባለሁ።
ዓመቱን ሙሉ እመላለሳለሁ፡፡ ስንተኛ ክፍል እንደሆንኩ አያውቁም። እድሜዬንም ይዘነጉታል። የትምህርት ቤት ስሜን ሁሉ የማስታውሳቸው እኔ ነኝ። የአባቴ ስም የባሏ ስም ነው።
"የማንም ዲቃላ አባት አይደለሁም:: አባትህን ሄደህ ፈልግ::"ይለኛል ከሷ ጋር ሲጣላ፡፡ እኔ ለነሱ የለሁም
👍2
ለእርሷም እንደዛው፡፡ አስረኛ ክፍል ስደርስ እሱ በጉበት ካንሰር ሞተ፡፡እናቴ ድንገት ካለችበት መጣች።
"ርቄ ልሄድ ነው።
" አለችኝ ከለቅሶው በኋላ፡፡
የት? ወዴት? ለምን? አላልኳትም፡፡ ምክንያቱም ወትሮም አልነበረችም፡፡ የነበረችባቸውንም ጊዜያት ቢሆን ህልውናዋ የለገሰኝ የማስታውሰው የጠራ ስሜት አልነበረኝም:: ትምህርት ቤት ደርሼ ስመለስ የለችም።አልጋዋ ላይ የተወሰነ ገንዘብ እና ደብዳቤ አስቀምጣልኛለች፡፡ የፃፈችልኝ እንዳልፈልጋት፣ ትምህርቴን እንድማር፣ ጎበዝ ልጅ እንድሆን፣ ሱስ እንዳቆም
እና እናት ስላልሆነችልኝ ይቅር እንድላት ነበር:: አልከፋኝም፡፡ ደስም አላለኝም።
ክልስ ነኝ፡፡ አባቴ ምናዊ እንደሆነ አላውቅም:: እንዴትስ ላውቅ
እችል ነበር?
"ይሄኔ እኮ የዘጋ ሀብታም ፈረንጅ ይሆናል አባትህ:" ይሉኛል አብሮ አደጎቼ በቀልድ: የሚጎፈንነኝ ቀልድ መሆኑ አይገባቸውም። የሚያውቁኝ ሰዎች ስለእናቴ ሲያጉረመርሙ እሰማለሁ።
ስለሽርሙጥናዋ፣ ስለቀያየረቻቸው ወንዶች፣ ስላገባቻቸው ባሎች፣ ስለሰራችባቸው ትልልቅ ሆቴሎች...።
ያስጠላኛል: ያስጠሉኛል፡፡ ሀሜትና እውነታውን መለየት አልችልም::
ምክንያቱም ስለእናቴ የማውቀው እውነትም የለኝማ! ከወንዶች በነበራት ግንኙነት ዛቢያ የሚውጠነጠነውን ሀሜት ግን እሷ አታደርገውም ማለት ይከብዳል። ምክንያቱም እናቴ
ሴሰኝነት መክሊቷ ነበር።
ከማላያት ወንድ ጋር አልነበረም። ስለቤተሰብ ትስስር ተያያዥ ነገር መስማትም ማየትም አልፈልግም። አንዳንዴ እውነት ግን አባቴ ክዶኝ ነው? ወይስ ጭራሽ መፈጠሬን አያውቅ ይሆን? ብዬ አስባለሁ። አላውቅም። የራሱ ጉዳይ!! ባሏ ከሞተ በኋላ
ቤተሰብ ብቻ ሳይሆን ጓደኛም የሌለኝ ሆንኩ፡፡ ከሱሴ ተጋባሁ።ከሱሶቼ ጋር በፍቅር ተቆራኘን። ከእንጀራ አባቴ ሱስ፣ ከእናቴ ሽፍደት፣ ከራሴ ቅጥ ያጣ ግድ የለሽነት አወጣጥቼ የአሁኑ ኪሩቤል ተሰራ።
"ኪሩ? አንተ ኪሩ?" ትከሻዬን እየወዘወዘች ጠራችኝ :: ስምሪት ናት። ቡና ልንጠጣ ተቀምጠናል።
"ፊትህ እኮ ደም መስሏል። ምን እያሰብክ ነው?" አለችኝ መልሳ።ከዚያን ቀን በኋላ በተገናኘን ቁጥር ደህና መሆኗን ልጠይቃት አስባለሁ። ልክ ሳያት
እተወዋለሁ፡፡ ልትጠይቀኝ የምትፈልገው ነገር ያላት ይመስለኛል:: ግን አትጠይቀኝም።እንደበፊቱ መጫወት አቃተን።
"ሴት ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ የተለየ ስሜት ሳትሰጠኝ አልቀረም::" አልኳት፡፡"
ተመስገን ነው:: እንዴት የተለየች ብትሆን ነው?" አለችኝ ምንም ጉጉት ሳያድርባት፡፡
"በማላውቀው ምክንያት እናቴን መሰለችኝ።"
"እናትህን እኮ አትወዳቸውም።" አለችኝ ሰውነቷ እየፈሰሰ እስኪመስለኝ ተኮማትራ።
"አዎን አልወዳትም::" የሚሰማኝን መግለፅ ከበደኝ።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
"ርቄ ልሄድ ነው።
" አለችኝ ከለቅሶው በኋላ፡፡
የት? ወዴት? ለምን? አላልኳትም፡፡ ምክንያቱም ወትሮም አልነበረችም፡፡ የነበረችባቸውንም ጊዜያት ቢሆን ህልውናዋ የለገሰኝ የማስታውሰው የጠራ ስሜት አልነበረኝም:: ትምህርት ቤት ደርሼ ስመለስ የለችም።አልጋዋ ላይ የተወሰነ ገንዘብ እና ደብዳቤ አስቀምጣልኛለች፡፡ የፃፈችልኝ እንዳልፈልጋት፣ ትምህርቴን እንድማር፣ ጎበዝ ልጅ እንድሆን፣ ሱስ እንዳቆም
እና እናት ስላልሆነችልኝ ይቅር እንድላት ነበር:: አልከፋኝም፡፡ ደስም አላለኝም።
ክልስ ነኝ፡፡ አባቴ ምናዊ እንደሆነ አላውቅም:: እንዴትስ ላውቅ
እችል ነበር?
"ይሄኔ እኮ የዘጋ ሀብታም ፈረንጅ ይሆናል አባትህ:" ይሉኛል አብሮ አደጎቼ በቀልድ: የሚጎፈንነኝ ቀልድ መሆኑ አይገባቸውም። የሚያውቁኝ ሰዎች ስለእናቴ ሲያጉረመርሙ እሰማለሁ።
ስለሽርሙጥናዋ፣ ስለቀያየረቻቸው ወንዶች፣ ስላገባቻቸው ባሎች፣ ስለሰራችባቸው ትልልቅ ሆቴሎች...።
ያስጠላኛል: ያስጠሉኛል፡፡ ሀሜትና እውነታውን መለየት አልችልም::
ምክንያቱም ስለእናቴ የማውቀው እውነትም የለኝማ! ከወንዶች በነበራት ግንኙነት ዛቢያ የሚውጠነጠነውን ሀሜት ግን እሷ አታደርገውም ማለት ይከብዳል። ምክንያቱም እናቴ
ሴሰኝነት መክሊቷ ነበር።
ከማላያት ወንድ ጋር አልነበረም። ስለቤተሰብ ትስስር ተያያዥ ነገር መስማትም ማየትም አልፈልግም። አንዳንዴ እውነት ግን አባቴ ክዶኝ ነው? ወይስ ጭራሽ መፈጠሬን አያውቅ ይሆን? ብዬ አስባለሁ። አላውቅም። የራሱ ጉዳይ!! ባሏ ከሞተ በኋላ
ቤተሰብ ብቻ ሳይሆን ጓደኛም የሌለኝ ሆንኩ፡፡ ከሱሴ ተጋባሁ።ከሱሶቼ ጋር በፍቅር ተቆራኘን። ከእንጀራ አባቴ ሱስ፣ ከእናቴ ሽፍደት፣ ከራሴ ቅጥ ያጣ ግድ የለሽነት አወጣጥቼ የአሁኑ ኪሩቤል ተሰራ።
"ኪሩ? አንተ ኪሩ?" ትከሻዬን እየወዘወዘች ጠራችኝ :: ስምሪት ናት። ቡና ልንጠጣ ተቀምጠናል።
"ፊትህ እኮ ደም መስሏል። ምን እያሰብክ ነው?" አለችኝ መልሳ።ከዚያን ቀን በኋላ በተገናኘን ቁጥር ደህና መሆኗን ልጠይቃት አስባለሁ። ልክ ሳያት
እተወዋለሁ፡፡ ልትጠይቀኝ የምትፈልገው ነገር ያላት ይመስለኛል:: ግን አትጠይቀኝም።እንደበፊቱ መጫወት አቃተን።
"ሴት ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ የተለየ ስሜት ሳትሰጠኝ አልቀረም::" አልኳት፡፡"
ተመስገን ነው:: እንዴት የተለየች ብትሆን ነው?" አለችኝ ምንም ጉጉት ሳያድርባት፡፡
"በማላውቀው ምክንያት እናቴን መሰለችኝ።"
"እናትህን እኮ አትወዳቸውም።" አለችኝ ሰውነቷ እየፈሰሰ እስኪመስለኝ ተኮማትራ።
"አዎን አልወዳትም::" የሚሰማኝን መግለፅ ከበደኝ።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍2
#የምሬት_ምስጋና
በቁርጥ የጠገበ ሲያቀርብ ምስጋና
ቆሎ ካፉ ያለ ይሄንን አየና
ቢያሰማ 'ሮሮ
በ'ድሉ ተማሮ
አምላክ ተደሰተ ከምስጋና ቆጥሮ
ፍላጎቱ ሞልቶ ካንገቱ ባይቀና
የአምሳሉ ፍጡር ነፍሱ ተርፏልና።
🔘በፋሲል ኀይሉ🔘
በቁርጥ የጠገበ ሲያቀርብ ምስጋና
ቆሎ ካፉ ያለ ይሄንን አየና
ቢያሰማ 'ሮሮ
በ'ድሉ ተማሮ
አምላክ ተደሰተ ከምስጋና ቆጥሮ
ፍላጎቱ ሞልቶ ካንገቱ ባይቀና
የአምሳሉ ፍጡር ነፍሱ ተርፏልና።
🔘በፋሲል ኀይሉ🔘
#ቀላውጦ_ማስመለስ
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
ግፈኛዋ እናቴን መሰልሽኝ፡፡ ግን በተለየ ወደድኩሽ፡ ነው የምላት? እንኳን ለርሷ ለራሴ የተደበላለቀ ነገር አለው። ለርሷ
ላስረዳት ቀርቶ ለራሴም አልገባኝም፡፡ እኔም አልገባኝም። ስምሪት ለምን እናቴን አስታወሰችኝ? “ስምረት ሞተች የሚለው
የአርሴማ ጥሪ የፈጠረብኝ ድንጋጤ እንዴት ብሽቅ ለሆነው የአሁኑ ስሜቴ ጎታች ምክንያት ሆነ? በውል ያልለየሁት
ለስምሪት የተሰማኝ ስሜት በምን ስሌት ወደልጅነት ትዝታዬ አሽመጠጠኝ? አላውቅም!! ምናልባት እስከማስታውሰው ለሰው ግድ የሰጠኝ በዚህ ክስተት ስለሆነ? ምናልባት ሰው መሆን ለሰው ማሰብን ያካትት ይሆን? ምናልባት ሰው ሆኜ ይሆን? ምናልባት ሰው በሆንኩ ቅፅበት እንደሰው ግድ ሳይሰጡኝ
ያለፍኳቸውን ክስተቶች ማሰላሰል መጀመሬ ይሆን? አላውቅም!!
ብቻ ምንም ሽራፊ ስሜት አይሰጠኝም ያልኳቸው ስንጣቂ የኑሮ ሰበዞቼን ሳይቀር ሳልፈልግ እያሰብኳቸው ነው።
"እያስጨነቅኩህ ነው?" አለችኝ ስምሪት ደጋግማ የማልወዳትን እናቴን እና የተለየ ስሜት የፈጠረችብኝን ሴት ምን
እንዳመሳሰላቸው ስትጠይቀኝ ቆይታ።
"እናቴን እንደማልወዳት እርግጠኛ እየሆንኩ አይደለም።" መለስኩላት። በእርግጥ የሚሰማኝ የትኛው እንደሆነ
አልለየሁትም። አቅፋኝ ታለቅስ ለነበረችው እናቴ ይሁን ቁብ ለማትሰጠኝ እናቴ የማልለየው ሀዘን ይቦረቡረኛል፡፡ ደግሞ
ተመልሶ የሚያንገሸግሽ ንዴት እና ጥላቻ ይግተለተልብኛል፡፡
ስምሪት ፀጥ አለችኝ፡፡ ዓይኖቿን አጥብባ ስታየኝ ቆየችና።
"ለምን አታረጋግጥም?" አለችኝ፡፡
"ምኑን?"
"ለእናትህ የሚሰማህን ስሜት?"
"እንዴት? በምን?"
“ፈልጋቸዋ!! ፈልገህ አግኛቸው።"
“የት ብዬ? ትሙት? ትኑር? እንኳን ማወቅ
ይከብዳል፡፡ብዙ ዓመት አልፏል።" ይሄን ለሷ ስመልስላት ራሴን ሰማሁት።ጥያቄዬ ልፈልጋት? ወይስ አልፈልጋት? የሚለውን እርከን አልፏል። 'አልፈልጋትም'የሚለውን
ጭራሽ አለማሰቤ አስገረመኝ። እሷም ይህ የገባት መሰለኝ፡፡ ፈጠን ብላ።
"ራስህን ዝግጁ ካደረግክ ፍንጭ የምናጣ አይመስለኝም::" አለችኝ
ዝግጁነቴን ለማረጋገጥ ነው መሰል ከአፌ የሚወጣውን ቃል አፏን ከፍታ እየጠበቀች፡፡ ፀጥ አልኩ። ፀጥ አለችኝ፡፡ እያየኋት እንደሆነ ሲገባት ታቀረቅራለች፡፡ እያየችኝ እንደሆነ ሳውቅ ዓይኖቼን በሌላ አቅጣጫ አርቄ እልካቸዋለሁ።
"ስምሪት?"
"አቤት?"
“እስኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ?" ራሷን በመነቅነቅ እንድቀጥል ተስማማችልኝ፡፡
"ለምንድነው ከሌላ ሰው በተለየ የምትቀርቢኝ? የምትሰሚኝ?
የምታወሪኝ?" የጠበቀችው ሌላ ጥያቄ እንደሆነ ሁሉ ፊቷ ረገበ።
ከአይምሮ ይልቅ ልብ ይማርከኛል፡፡" መልሷ እርግጠኛነት ነበረው፡፡
"ማለት?"
| “ከእውቀት ይልቅ ለቅንነት ዋጋ እሰጣለሁ ማለት ነዋ!! ቅንነት የሌለበት እውቀት በዜሮ ይባዛብኛል፡፡ቅንነት የሞላበት አለማወቅ እንኳን ይገዛኛል። ልብህ ቅን ነው::" ብላኝ ከኔ መልስ
እንደማትጠብቅ ተደላደለች። እሷ በገለፀችኝ ልክ ልበ ቅን መሆኔን እጠራጠራለሁ። ምክንያቱም ቅንነት ይመነዘራል ይመስለኛል፡፡ እኔ ስለራሴ እስከማውቀው ከራሴ ውጪ ለማንም
ግድ ኖሮኝ ለሰዎች ቀና ለማድረግም ሆነ ቀና ለማስብ ተጨንቄ አላውቅም። ማንም ጉዳዬ አይደለም።እሷ ሁሌም እንደዚህ ናት፡፡ ስለእኔ ስታወራ ባለቤቱ እርግጠኛ ከሆንኩት በላይ እርግጠኛ ናት፡፡ ምናልባት እኔ ራሴን ከማዳምጠው በላይ እሷ ስለምታዳምጠኝ ይሆናል። ሁሌም የምትጠቁመኝ ኪሩቤል መድረስ የሚችልበትን ጫፍ እንጂ ሰዎች ወይ እሷ መዳረሻ ብለው የሰቀሉትን ጫፍ አይደለም።
"ስምሪት?" ባልጠራትም እየሰማችኝ እንደሆነ አውቃለሁ።ከእስከዛሬው ሁሉ በተለየ እንድትሰማኝ ፈለግኩ፡፡
"አቤት?"
“ከዛን ቀን በኋላ አንቺን እንደአለቃዬ ወይም እንደጓደኛዬ ማሰብ እየቻልኩ አይደለም።" አልኳት። ከአፌ እስኪወጣ እየጠበቀችው ያለ ንግግር እንደሆነ ሁሉ መገረምም መደንገጥም ሳይታይባት
"አንድ እርምጃ ጠልቀህ ያወቅከኝ ስለመሰለህ ነው?" መልስ
የምትፈልግም አትመስልም።
“ማለት?" አልኳት ያለችው ሳይገባኝ ቀርቶ ሳይሆን የማስረዳት አቅም ከድቶኝ፡፡
"ኪሩ ልብሳቸውን ስትገፍ ያወቅካቸው እንደሚመስሉህ ሴቶች እርቃኔን ስላየኸኝ ገበናዬን የገለብክ አይምሰልህ፡፡"
የምታወራበት ቅላፄ የማላውቀውና ምሬት የተቀላቀለበት ነው፡፡ ምን
እንደምላት እና ለሷና ለማውቃቸው ሴቶች የሚሰማኝን የአንድ ጤፍ ፍሬና የተራራ ያህል የገዘፈ የስሜት ልዩነት ማስረዳት ባለመቻሌ ተናደድኩ።
"እንደዛ አይደለም የተሰማኝ። ውስጤ የቀረውን የገላሽን ምስል ሳስበው አብሬሽ መተኛት አይደለም የሚሰማኝ፡፡ ተሰምቶኝ በማያውቅ መልኩ ከወለሉ ላይ አንስቼሽ አልጋ ላይ ያደረስኩሽ ቅፅበት የእድሜ ዘመኔን ያህል ረዥም እንዲሆን ነው የሚሰማኝ፡፡ ክንዴ ላይ እንዳቀፍኩሽ የተከደኑ ዓይኖችሽን በስስት እያየሁ ዘመኖቼ ቢያልቁ ነው የተሰማኝ፡፡” ይግባት አይግባት እንጃ ከዚህ በላይ ማስረዳት ግን አቃተኝ፡፡ ደቂቃዎችን ትንፋሽ ያጠረኝ እስኪመስለኝ ፀጥ አለች፡፡
ሲገባኝ ሁሉም ሰው የሆነች "የለውጥ ኩርባ" አለችው።አስተሳሰቡ ወይ ስሜቱ፡ ወይ ድርጊቱ የሚቀየርባት።ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚታጠፍበት ወይም ከወደቀበት መቀመቅ የሚስፈነጠርበት ወይም ለዛለው ጉልበቱ አቅም የሚያገኝበት፡፡ለውጥ ወደ ተሻለ ማደግ ብቻ አይደለምና ኩርባውን ሲታጠፍ
ውድቀትም ሊሆን ይችላል፡፡ ያቺ የለውጥ ኩርባ አንድ የሆነች ኢምንት ክስተት ልትሆን ትችላለች ወይም ዓረፍተ ነገር ወይም አንዲት ቃል ምናልባት አንዲት መሳም ወይም የአንዲት ደቂቃ
መታቀፍ ወይም...
የኔ የለውጥ ኩርባ ያቺ ቀን ነበረች።
"ልክ አይሆንም። እኔና አንተ ከዚህ ቀደም ከነበረን የዘለለ ግንኙነት ሊኖረን አይችልም::" አለችኝ፡፡
"ቅድም 'ከአእምሮ ይልቅ ልብ ይማርከኛል አልሺኝ አይደል?
" እህ... " የምቀጥለውን ለመስማት እየሰገገች።
"ሲገባኝ ሌላ ፍቺው ከስሌት ይልቅ ለስሜት ቅርብ ነኝ ማለትሽ መሰለኝ፡፡ ልክና ስህተቱን በስሌት ልቀምርልሽ አልችልም። ባንቺ ፍቅር ከመውደቅ በላይ ልክ የሆነ ስሜት ተሰምቶኝ እንደማያውቅ ግን ላረጋግጥልሽ፡፡" አልኳት አሁንም ምን ያህል እንተረዳችኝ ባይገባኝም።
"ምናልባት እስክጋደምልህ ይሆናል። ፍላጎትህ እስኪረግብ!"ከአፉ የሚወጣው ቃልም ድምፀትም የሷ አይመስልም:: ጥርሷን እያፏጨች ነው የተናገረችው። በመጀመሪያ ደነገጥኩ፡፡ ስምሪት
እንዲህ ስትናገር ሰምቼ አላውቅም:: በመቀጠል ተናደድኩ።በፍፁም እየተረዳችኝ አልነበረም።በመሰለስ ግን ስለዚህች ሴት የማላውቀው ብዙ ነገር መኖሩን ማሰብ ጀመርኩ፡፡
ስደነግጥ
ለኔ ሳይሆን ለእርሷ ማንነት የማይመጥናት የመሰሉኝን ቃላቶች
በማውራቷ ዓይኖቼን ጎልጎዬ አፈጠጥኩባት።
ስናደድ
“እየገባሁሽ አይደለም።ስለሴክስ እያወራሁ አይደለም። እዚህ ጋር(ልቤን በእጄ ደግፌ) ስለሚሰማኝ ስሜት ነው እየነገርኩሽ የነበረው።" አልኳት በአፏ አልመለሰችልኝም:: ፊቷ ግን ስልችት
አሳየኝ፡፡
ማሰብ ስጀምር
"ማነው?" አልኳት
“ማን?" መለሰችልኝ
እንዲህ እንዲሰማሽ ያደረገሽ?" በረዥሙ ተንፍሳ ፀጥ አለች።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
፡
፡
#ክፍል_ስድስት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
ግፈኛዋ እናቴን መሰልሽኝ፡፡ ግን በተለየ ወደድኩሽ፡ ነው የምላት? እንኳን ለርሷ ለራሴ የተደበላለቀ ነገር አለው። ለርሷ
ላስረዳት ቀርቶ ለራሴም አልገባኝም፡፡ እኔም አልገባኝም። ስምሪት ለምን እናቴን አስታወሰችኝ? “ስምረት ሞተች የሚለው
የአርሴማ ጥሪ የፈጠረብኝ ድንጋጤ እንዴት ብሽቅ ለሆነው የአሁኑ ስሜቴ ጎታች ምክንያት ሆነ? በውል ያልለየሁት
ለስምሪት የተሰማኝ ስሜት በምን ስሌት ወደልጅነት ትዝታዬ አሽመጠጠኝ? አላውቅም!! ምናልባት እስከማስታውሰው ለሰው ግድ የሰጠኝ በዚህ ክስተት ስለሆነ? ምናልባት ሰው መሆን ለሰው ማሰብን ያካትት ይሆን? ምናልባት ሰው ሆኜ ይሆን? ምናልባት ሰው በሆንኩ ቅፅበት እንደሰው ግድ ሳይሰጡኝ
ያለፍኳቸውን ክስተቶች ማሰላሰል መጀመሬ ይሆን? አላውቅም!!
ብቻ ምንም ሽራፊ ስሜት አይሰጠኝም ያልኳቸው ስንጣቂ የኑሮ ሰበዞቼን ሳይቀር ሳልፈልግ እያሰብኳቸው ነው።
"እያስጨነቅኩህ ነው?" አለችኝ ስምሪት ደጋግማ የማልወዳትን እናቴን እና የተለየ ስሜት የፈጠረችብኝን ሴት ምን
እንዳመሳሰላቸው ስትጠይቀኝ ቆይታ።
"እናቴን እንደማልወዳት እርግጠኛ እየሆንኩ አይደለም።" መለስኩላት። በእርግጥ የሚሰማኝ የትኛው እንደሆነ
አልለየሁትም። አቅፋኝ ታለቅስ ለነበረችው እናቴ ይሁን ቁብ ለማትሰጠኝ እናቴ የማልለየው ሀዘን ይቦረቡረኛል፡፡ ደግሞ
ተመልሶ የሚያንገሸግሽ ንዴት እና ጥላቻ ይግተለተልብኛል፡፡
ስምሪት ፀጥ አለችኝ፡፡ ዓይኖቿን አጥብባ ስታየኝ ቆየችና።
"ለምን አታረጋግጥም?" አለችኝ፡፡
"ምኑን?"
"ለእናትህ የሚሰማህን ስሜት?"
"እንዴት? በምን?"
“ፈልጋቸዋ!! ፈልገህ አግኛቸው።"
“የት ብዬ? ትሙት? ትኑር? እንኳን ማወቅ
ይከብዳል፡፡ብዙ ዓመት አልፏል።" ይሄን ለሷ ስመልስላት ራሴን ሰማሁት።ጥያቄዬ ልፈልጋት? ወይስ አልፈልጋት? የሚለውን እርከን አልፏል። 'አልፈልጋትም'የሚለውን
ጭራሽ አለማሰቤ አስገረመኝ። እሷም ይህ የገባት መሰለኝ፡፡ ፈጠን ብላ።
"ራስህን ዝግጁ ካደረግክ ፍንጭ የምናጣ አይመስለኝም::" አለችኝ
ዝግጁነቴን ለማረጋገጥ ነው መሰል ከአፌ የሚወጣውን ቃል አፏን ከፍታ እየጠበቀች፡፡ ፀጥ አልኩ። ፀጥ አለችኝ፡፡ እያየኋት እንደሆነ ሲገባት ታቀረቅራለች፡፡ እያየችኝ እንደሆነ ሳውቅ ዓይኖቼን በሌላ አቅጣጫ አርቄ እልካቸዋለሁ።
"ስምሪት?"
"አቤት?"
“እስኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ?" ራሷን በመነቅነቅ እንድቀጥል ተስማማችልኝ፡፡
"ለምንድነው ከሌላ ሰው በተለየ የምትቀርቢኝ? የምትሰሚኝ?
የምታወሪኝ?" የጠበቀችው ሌላ ጥያቄ እንደሆነ ሁሉ ፊቷ ረገበ።
ከአይምሮ ይልቅ ልብ ይማርከኛል፡፡" መልሷ እርግጠኛነት ነበረው፡፡
"ማለት?"
| “ከእውቀት ይልቅ ለቅንነት ዋጋ እሰጣለሁ ማለት ነዋ!! ቅንነት የሌለበት እውቀት በዜሮ ይባዛብኛል፡፡ቅንነት የሞላበት አለማወቅ እንኳን ይገዛኛል። ልብህ ቅን ነው::" ብላኝ ከኔ መልስ
እንደማትጠብቅ ተደላደለች። እሷ በገለፀችኝ ልክ ልበ ቅን መሆኔን እጠራጠራለሁ። ምክንያቱም ቅንነት ይመነዘራል ይመስለኛል፡፡ እኔ ስለራሴ እስከማውቀው ከራሴ ውጪ ለማንም
ግድ ኖሮኝ ለሰዎች ቀና ለማድረግም ሆነ ቀና ለማስብ ተጨንቄ አላውቅም። ማንም ጉዳዬ አይደለም።እሷ ሁሌም እንደዚህ ናት፡፡ ስለእኔ ስታወራ ባለቤቱ እርግጠኛ ከሆንኩት በላይ እርግጠኛ ናት፡፡ ምናልባት እኔ ራሴን ከማዳምጠው በላይ እሷ ስለምታዳምጠኝ ይሆናል። ሁሌም የምትጠቁመኝ ኪሩቤል መድረስ የሚችልበትን ጫፍ እንጂ ሰዎች ወይ እሷ መዳረሻ ብለው የሰቀሉትን ጫፍ አይደለም።
"ስምሪት?" ባልጠራትም እየሰማችኝ እንደሆነ አውቃለሁ።ከእስከዛሬው ሁሉ በተለየ እንድትሰማኝ ፈለግኩ፡፡
"አቤት?"
“ከዛን ቀን በኋላ አንቺን እንደአለቃዬ ወይም እንደጓደኛዬ ማሰብ እየቻልኩ አይደለም።" አልኳት። ከአፌ እስኪወጣ እየጠበቀችው ያለ ንግግር እንደሆነ ሁሉ መገረምም መደንገጥም ሳይታይባት
"አንድ እርምጃ ጠልቀህ ያወቅከኝ ስለመሰለህ ነው?" መልስ
የምትፈልግም አትመስልም።
“ማለት?" አልኳት ያለችው ሳይገባኝ ቀርቶ ሳይሆን የማስረዳት አቅም ከድቶኝ፡፡
"ኪሩ ልብሳቸውን ስትገፍ ያወቅካቸው እንደሚመስሉህ ሴቶች እርቃኔን ስላየኸኝ ገበናዬን የገለብክ አይምሰልህ፡፡"
የምታወራበት ቅላፄ የማላውቀውና ምሬት የተቀላቀለበት ነው፡፡ ምን
እንደምላት እና ለሷና ለማውቃቸው ሴቶች የሚሰማኝን የአንድ ጤፍ ፍሬና የተራራ ያህል የገዘፈ የስሜት ልዩነት ማስረዳት ባለመቻሌ ተናደድኩ።
"እንደዛ አይደለም የተሰማኝ። ውስጤ የቀረውን የገላሽን ምስል ሳስበው አብሬሽ መተኛት አይደለም የሚሰማኝ፡፡ ተሰምቶኝ በማያውቅ መልኩ ከወለሉ ላይ አንስቼሽ አልጋ ላይ ያደረስኩሽ ቅፅበት የእድሜ ዘመኔን ያህል ረዥም እንዲሆን ነው የሚሰማኝ፡፡ ክንዴ ላይ እንዳቀፍኩሽ የተከደኑ ዓይኖችሽን በስስት እያየሁ ዘመኖቼ ቢያልቁ ነው የተሰማኝ፡፡” ይግባት አይግባት እንጃ ከዚህ በላይ ማስረዳት ግን አቃተኝ፡፡ ደቂቃዎችን ትንፋሽ ያጠረኝ እስኪመስለኝ ፀጥ አለች፡፡
ሲገባኝ ሁሉም ሰው የሆነች "የለውጥ ኩርባ" አለችው።አስተሳሰቡ ወይ ስሜቱ፡ ወይ ድርጊቱ የሚቀየርባት።ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚታጠፍበት ወይም ከወደቀበት መቀመቅ የሚስፈነጠርበት ወይም ለዛለው ጉልበቱ አቅም የሚያገኝበት፡፡ለውጥ ወደ ተሻለ ማደግ ብቻ አይደለምና ኩርባውን ሲታጠፍ
ውድቀትም ሊሆን ይችላል፡፡ ያቺ የለውጥ ኩርባ አንድ የሆነች ኢምንት ክስተት ልትሆን ትችላለች ወይም ዓረፍተ ነገር ወይም አንዲት ቃል ምናልባት አንዲት መሳም ወይም የአንዲት ደቂቃ
መታቀፍ ወይም...
የኔ የለውጥ ኩርባ ያቺ ቀን ነበረች።
"ልክ አይሆንም። እኔና አንተ ከዚህ ቀደም ከነበረን የዘለለ ግንኙነት ሊኖረን አይችልም::" አለችኝ፡፡
"ቅድም 'ከአእምሮ ይልቅ ልብ ይማርከኛል አልሺኝ አይደል?
" እህ... " የምቀጥለውን ለመስማት እየሰገገች።
"ሲገባኝ ሌላ ፍቺው ከስሌት ይልቅ ለስሜት ቅርብ ነኝ ማለትሽ መሰለኝ፡፡ ልክና ስህተቱን በስሌት ልቀምርልሽ አልችልም። ባንቺ ፍቅር ከመውደቅ በላይ ልክ የሆነ ስሜት ተሰምቶኝ እንደማያውቅ ግን ላረጋግጥልሽ፡፡" አልኳት አሁንም ምን ያህል እንተረዳችኝ ባይገባኝም።
"ምናልባት እስክጋደምልህ ይሆናል። ፍላጎትህ እስኪረግብ!"ከአፉ የሚወጣው ቃልም ድምፀትም የሷ አይመስልም:: ጥርሷን እያፏጨች ነው የተናገረችው። በመጀመሪያ ደነገጥኩ፡፡ ስምሪት
እንዲህ ስትናገር ሰምቼ አላውቅም:: በመቀጠል ተናደድኩ።በፍፁም እየተረዳችኝ አልነበረም።በመሰለስ ግን ስለዚህች ሴት የማላውቀው ብዙ ነገር መኖሩን ማሰብ ጀመርኩ፡፡
ስደነግጥ
ለኔ ሳይሆን ለእርሷ ማንነት የማይመጥናት የመሰሉኝን ቃላቶች
በማውራቷ ዓይኖቼን ጎልጎዬ አፈጠጥኩባት።
ስናደድ
“እየገባሁሽ አይደለም።ስለሴክስ እያወራሁ አይደለም። እዚህ ጋር(ልቤን በእጄ ደግፌ) ስለሚሰማኝ ስሜት ነው እየነገርኩሽ የነበረው።" አልኳት በአፏ አልመለሰችልኝም:: ፊቷ ግን ስልችት
አሳየኝ፡፡
ማሰብ ስጀምር
"ማነው?" አልኳት
“ማን?" መለሰችልኝ
እንዲህ እንዲሰማሽ ያደረገሽ?" በረዥሙ ተንፍሳ ፀጥ አለች።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍4
#ቀላውጦ_ማስመለስ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
"እንዲህ እንዲሰማሽ ያደረገሽ?"በረዥሙ ተንፍሳ ፀጥ አለች።
"ድብቅ ነሽ።" አልኳት።
"ድብቅ እንኳን አይደለሁም::"
መለሰችልኝ፡፡
"እኔ የማልነግርሽ ክስተትም ስሜትም ኖሮኝ አያውቅም፡፡ ስላንቺ
አንዲትም ነገር አውርተሽ አታውቂም።"
"ጠይቀኸኝ አታውቅም፡፡ ለራሴ ቦታ አለኝ፡፡ ዋጋ የሌለኝ ሰው ጋ ራሴን የምጥል ርካሽ አይደለሁም::" ያለችው በትክክል ገብቶኝ እንደሆነ እርግጠኛ አልነበርኩም።
"አቤት? ዋጋ ባልሰጥሽ ኖሮ ስለራሴስ አወራሽ ነበር?"
"ዋጋ ስለሰጠኸኝ ሳይሆን ዋጋ ስለሰጠሁህ ነው ያወራኸኝ፡፡
ከሴቶችህ ብዙዎቹ ስለራሳቸው ነግረውናል፡፡ አንተ ግን ስለራስህ
ለአንዳቸውም ነግረህ አታውቅም። ለምን ይመስልሃል?ልትሰማቸው እንጂ ሊሰሙህ ጊዜያቸውንም ልባቸውንም አልሰጡህም። ወይም እንደዛ አስበሃል።" ከተናገረችው ሁሉ የገባኝ(ቃል በቃል ባትለውም) ልቤን ሰጥቼሃለሁ' ያለችው ነው።
"አሁን ልሰማሽ ዝግጁ ነኝ፡፡ ንገሪኝ! "
"አሁን ሰዓት ሄዷል። ወደ ቢሮ እንመለስ!" አለች በዓይኗ አስተናጋጅ እየፈለገች። ፍቅር የብዙ ነገር ቁልፍ መሆኑ ገባኝ
መሰለኝ፡፡ አስቤ ስለማላውቃቸው ብዙ ነገሮች ማሰብ ጀመርኩ፡፡
ከመለዮዬ ውጪ ምን ስለመልበስ አስቤ የማላውቀው ሰው ራሴን ልብሶች ስሸምት አገኘሁት።ያንተ ተክለ ሰውነት ልብስ ያስጌጣል እንጂ አንተን ልብሱ አያስጌጥህም፡፡ ለምትለብሰው መጠንቀቅ አይጠበቅብህም።"ብላኛለች ስምሪት ከመለዮዬ ሌላ ለብሼ ያየችኝ የመጀመሪያ ቀን፡፡
“ለምን እራቁቴን አታዪኝም?"
"አትባልግ እንግዲህ!"
በሌላ ቀን ለአንዲትም ቀን አስቤው የማላውቀውን ራሴን ቤተክርስቲያን ስፀልይ አገኘሁት፡፡ (በእርግጥ ከፀሎት ይልቅ ለንግግር የቀረበ ነገር ነበር) ፍቅር የሁሉ ነገር ቁልፍ መሆኑ መሰለኝ፡፡ የሁሉንም የህይወት ጥጎች ማጠንጠን ጀመርኩ።እስካሁን አንድ የሆነ ቦታ ላይ የሆነ እድሜዬ ላይ ቆሜ የነበር አይነት ስሜት ነበር የሚሰማኝ፡፡ ገና አሁን በስምሪት ፍቅር መኖርን የጀመርኩ፡፡ በገፋችኝ መጠን ወደርሷ የሚስበኝ ፍቅሯ
ልቤን ከብዶት ይጎትተኝ ጀመረ።ቀናቶች የንስር ክንፍ አውጥተው ይበራሉ እሷ በቻለችው መጠን ትሸሸኛለች እኔ ደግሞ ከምችለው በላይ ወደርሷ እወነጨፋለሁ። የምንገናኝባቸውን እና ልናወራ የምንችልባቸውን አጋጣሚዎች
ትዘጋቸዋለች።
ከነገ ጀምሮ እረፍት ወጣለሁ::" አለችኝ የሆነ ቀን የቀኑ ስራ ማብቂያ ሰዓት ላይ እየወጣን።
"ለምን? ሽሽት ነው?" አልኳት።
የምን ሽሽት? ማረፍ ፈልጌ ነው።" አለችኝ ዓይኖቼን እየሸሸች።ቆምኩኝ ቆመች አየኋት አቀረቀረች የጡቷቿ ጫፎች ደረቴን እስኪነኩት ተጠጋኋት። አልሸሸችኝም።ምንም እንቅስቃሴ አላደረገችም፡፡ ወደ ጆሮዋ ከንፈሮቼን አስጠግቼ “ታውቂያለሽ? ሁሌም አንድ እርምጃ ወደፊት የማያራምደን
የ'ባይሳካስ?” ፍርሃት ነው። እመኚኝ!! እመኚኝና ልብሽን ስጪኝ። አንድ ነገር ቃል እገባልሻለሁ። ልብሽን አልሰብርም
አልኳት። ዓይኗን ገርበብ አድርጋ ነበር የሰማችኝ ከመግለጧ በፊት አየኋት፡፡ ዓይኔ ከንፈሯ ላይ ቀረ። ውጤቱን ማሰብ
አልፈለግኩም።ወይም ምንም ቢሆን ግድ አልነበረኝም።
ከንፈሮቿን ሳምኳቸው። ለምን ያህል ሰከንድ እንደሆነ ባላውቅም
መልሳ ስማኛለች፡፡ እጇ በወገቤ ዙሪያ አልፏል። ይሄን ያሰብኩት ድንገት አቁማ ገፍታኝ ስትቆም እንጂ ስትስመኝ
ከጥፍጥናዋ ውጪ ማወቅ የቻልኩት ነገር አልነበረም።
“ኪሩ? ምንድነው የምታደርገው?" ጮኸችብኝ፡፡ ፈገግ አልኩ። ልቧን ስትሰማው ስማኛለች፡፡ መንገድ ላይ መሆናችን እንኳን አላሳሰባትም ነበር፡፡ አዕምሮዋን ስትሰማው ነው የገፋችኝ።
ባትነግረኝም የማትክደው ስሜት አላት። ፈገግታዬ አበሳጫት። ተናደደች።
"ኪሩ ሁለተኛ እንዲህ ብታደርግ እንጣላለን። የምሬን ነው!!"
አለች ድርጊቴ እንዳናደዳት ለመግለፅ እየጣረች።
"እሺ፡፡ ከዛሬ በኋላ ራስሽ ካልጠየቅሽኝ አላደርገውም::"
"ማለት?"
ኪሩቤል ሳመኝ ብለሽ አፍ አውጥተሽ ካልጠየቅሽኝ አልስምሽም።" አልኳት።
ወገኛ! ኪሩ እኔ አንተ እንደምታውቃቸው አይነት ሴቶች አይደለሁም።" አለች መንገድ እየጀመረች።
"አውቃለሁ!! ከነሱ የሚለይሽ ነገር ባይኖር ከነሱ የተለየ ስሜት
አትሰጪኝም ነበር።" መለስኩላት እርምጃዬን ከርሷ ጋር እያመጣጠንኩ።
'ለምን እኔን? ለምን? ደግሞስ ለምን አሁን? አንተ ማንም ሴት የምትደነግጥልህ ወንድ ነህ!"
"ማንም ሴት ደንግጣልኝ ይሆናል፡፡ ካንቺ ውጪ ያስደነገጠችኝ ሴት የለችም ለውጡ እንዴት አይታይሽም?" አልኳት።
ተለይታኝ ሄደችበልቤ። ተሸክሜያት ወደ ሱሴ ሄድኩ። በቀኖችህ ውስጥ ለምታደርገው ትግል ጥያቄው መሸነፍህ አይደለም።መዋጋትህ እንጂ ምክንያቱም ሳትታገል ሁሌም ውጤቱ የታወቀ ነው። ተሸናፊ ነህ። በትግልህ ውስጥ ውጤቱ ከሁለት አንዱ ነው። ማሸነፍ ወይም መሸነፍ!! ጥያቄው መዋጋትህ ላይሆን ይችላል የተዋጋህለት አላማ እንጂ። እሷ ናት። ምንንም ባልፍላት የሚገባት። እረፍት መውጣቷን ተከትሎ ናፍቆቷን መታገስ ከምችለው በላይ ነበረ። ስልኳ እረፍት ከወጣችበት ቀን ጀምሮ ዝግ ነው።ጭንቅላቴ የሚፈነዳ መሰለኝ፡፡
እቤቷ ላለመሄድ ከቁጥር በላይ ለሆነ ጊዜ አመነታሁኝ።
በስምንተኛው ቀን እሷን ሳላያት ባድር ትንፋሼ ቆሞ የማድር መሰለኝ።ከስራ ወጥቼ እቤቷ ሄድኩ:: በሩን ስትከፍትልኝ ምን እንደምላት፣ምን ለብሳ እንደማገኛት፣ ስታየኝ ምን እንደሚሰማት እያሰብኩ በሩን በስሱ ቆረቆርኩ ደገምኩት።ጨዋታ አቋርጦ እንደከፈተልኝ የሚያስታውቅ ሰው ያላለቀ ሳቁን እየቀጠለ በሩን ከፈተልኝ።
"አቤት?" አለኝ።
ሰምቼዋለሁ ዝም አልኩ፡፡ ደገመልኝ፡፡ ዝምታዬን ደገምኩለት።ስምሪት ከጀርባው ብቅ አለች። ምንም አይነት የፊት ሜክአፕ
ስትጠቀም አይቻት አላውቅም።ተቀባብታ ሌላ ሴት መስላለች፡፡ከከንፈሯ ውጪ ያልደመቀ የለም:: ለፓንትነት የቀረበ ቁምጣ እና ለጡት ማስያዣነት የቀረበ ሹራብ ለብሳለች። ፀጉሯ ቢመሳቀልም ተለቋል።እሱን አየሁት።በሲሊፐር ነው።
እንግድነት አይታይበትም።የከንፈሩ ጠርዝ ላይ አስተዋልኩ። ስምሪት ያስደነገጣት የኔ መምጣት ይሆን ወይም የመጣሁበት ሰዓት አላውቅም ደንግጣለች፡፡
"እንዴ? ኪሩቤል?" እየተንተባተበች ጨበጠችኝ፡፡
ሰውየው ለኔ ማሳወቅ የፈለገው ነገር ያለ መሰለኝ አቅፎ ወደ ራሱ አስጠግቶ ፀጉሯን ሳማት፡፡ እሷ በድርጊቱ ያፈረች መሰለኝ ዓይኔን ሸሸችው።
"ማሬ የስራ ባልደረባዬ ነው።" አለች ለሰውየው።ለኔ ደግሞ "የአርሴማ አባት ነው::" ተጨባበጥን።
“ኦው ፖሊስ ነህ? የሆሊውድ አክተር ነበር የመሰልከኝ፡፡ ሃሃሃ" ሰውየው መቀለዱ ነው።በቡጢ ዱልዱም አፍንጫውን ባጠፋለት ደስ እንደሚለኝ ቢያውቅ፡፡ በዚህ መሃል አርሴማ ዓይኗን እያሻሸች በአባቷና በእናቷ እግር መሃል ብቅ አለች። ስታየኝ ፈገግ ማለቷ ያስታወሰችኝ ስለመሰለኝ ደስ አለኝ። ልስማት
ስጠጋት ግን ሸሸችኝ፡፡
“ይቅርታ በማይሆን ሰዓት መጣሁ መሰለኝ። የስራ ጉዳይ እቤት ድረስ ይዤ መምጣት አልነበረብኝም::" መናገር ስለነበረብኝ አልኩኝ እንጂ እግሬ ከመሬቱ ጋር ያዛመደው ነገር ያለ ይመስል
አልተንቀሳቀስኩም።ሰውየው እንድገባ ጋበዘኝ፡፡ ለአፉ እንዳለው ያስታውቅበታል፡፡ተሰናብቻቸው እግሬን ከተተከለበት አንቀሳቅሼ በመጣሁበት አቅጣጫ መራሁት። አለመታደል ነው #ቀላውጦ_ማስመለስ ትል ነበር እናቴ፡፡ የምፈልገው ስለርሷ አለማስብ ነው። የማደርገው ግን ተቃራኒውን ነው
የጠራችው ሰውየው የስራ ባልደረባዋ መሆኔን እንዲያምናት ብቻ ነው? ድምፅዋ ውስጥ ለምን ፍርሃት ሰማሁ? ለምን ባለቤቴ ነው አላለችኝም የዛን
እለት አርሴማ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#በሜሪ_ፈለቀ
"እንዲህ እንዲሰማሽ ያደረገሽ?"በረዥሙ ተንፍሳ ፀጥ አለች።
"ድብቅ ነሽ።" አልኳት።
"ድብቅ እንኳን አይደለሁም::"
መለሰችልኝ፡፡
"እኔ የማልነግርሽ ክስተትም ስሜትም ኖሮኝ አያውቅም፡፡ ስላንቺ
አንዲትም ነገር አውርተሽ አታውቂም።"
"ጠይቀኸኝ አታውቅም፡፡ ለራሴ ቦታ አለኝ፡፡ ዋጋ የሌለኝ ሰው ጋ ራሴን የምጥል ርካሽ አይደለሁም::" ያለችው በትክክል ገብቶኝ እንደሆነ እርግጠኛ አልነበርኩም።
"አቤት? ዋጋ ባልሰጥሽ ኖሮ ስለራሴስ አወራሽ ነበር?"
"ዋጋ ስለሰጠኸኝ ሳይሆን ዋጋ ስለሰጠሁህ ነው ያወራኸኝ፡፡
ከሴቶችህ ብዙዎቹ ስለራሳቸው ነግረውናል፡፡ አንተ ግን ስለራስህ
ለአንዳቸውም ነግረህ አታውቅም። ለምን ይመስልሃል?ልትሰማቸው እንጂ ሊሰሙህ ጊዜያቸውንም ልባቸውንም አልሰጡህም። ወይም እንደዛ አስበሃል።" ከተናገረችው ሁሉ የገባኝ(ቃል በቃል ባትለውም) ልቤን ሰጥቼሃለሁ' ያለችው ነው።
"አሁን ልሰማሽ ዝግጁ ነኝ፡፡ ንገሪኝ! "
"አሁን ሰዓት ሄዷል። ወደ ቢሮ እንመለስ!" አለች በዓይኗ አስተናጋጅ እየፈለገች። ፍቅር የብዙ ነገር ቁልፍ መሆኑ ገባኝ
መሰለኝ፡፡ አስቤ ስለማላውቃቸው ብዙ ነገሮች ማሰብ ጀመርኩ፡፡
ከመለዮዬ ውጪ ምን ስለመልበስ አስቤ የማላውቀው ሰው ራሴን ልብሶች ስሸምት አገኘሁት።ያንተ ተክለ ሰውነት ልብስ ያስጌጣል እንጂ አንተን ልብሱ አያስጌጥህም፡፡ ለምትለብሰው መጠንቀቅ አይጠበቅብህም።"ብላኛለች ስምሪት ከመለዮዬ ሌላ ለብሼ ያየችኝ የመጀመሪያ ቀን፡፡
“ለምን እራቁቴን አታዪኝም?"
"አትባልግ እንግዲህ!"
በሌላ ቀን ለአንዲትም ቀን አስቤው የማላውቀውን ራሴን ቤተክርስቲያን ስፀልይ አገኘሁት፡፡ (በእርግጥ ከፀሎት ይልቅ ለንግግር የቀረበ ነገር ነበር) ፍቅር የሁሉ ነገር ቁልፍ መሆኑ መሰለኝ፡፡ የሁሉንም የህይወት ጥጎች ማጠንጠን ጀመርኩ።እስካሁን አንድ የሆነ ቦታ ላይ የሆነ እድሜዬ ላይ ቆሜ የነበር አይነት ስሜት ነበር የሚሰማኝ፡፡ ገና አሁን በስምሪት ፍቅር መኖርን የጀመርኩ፡፡ በገፋችኝ መጠን ወደርሷ የሚስበኝ ፍቅሯ
ልቤን ከብዶት ይጎትተኝ ጀመረ።ቀናቶች የንስር ክንፍ አውጥተው ይበራሉ እሷ በቻለችው መጠን ትሸሸኛለች እኔ ደግሞ ከምችለው በላይ ወደርሷ እወነጨፋለሁ። የምንገናኝባቸውን እና ልናወራ የምንችልባቸውን አጋጣሚዎች
ትዘጋቸዋለች።
ከነገ ጀምሮ እረፍት ወጣለሁ::" አለችኝ የሆነ ቀን የቀኑ ስራ ማብቂያ ሰዓት ላይ እየወጣን።
"ለምን? ሽሽት ነው?" አልኳት።
የምን ሽሽት? ማረፍ ፈልጌ ነው።" አለችኝ ዓይኖቼን እየሸሸች።ቆምኩኝ ቆመች አየኋት አቀረቀረች የጡቷቿ ጫፎች ደረቴን እስኪነኩት ተጠጋኋት። አልሸሸችኝም።ምንም እንቅስቃሴ አላደረገችም፡፡ ወደ ጆሮዋ ከንፈሮቼን አስጠግቼ “ታውቂያለሽ? ሁሌም አንድ እርምጃ ወደፊት የማያራምደን
የ'ባይሳካስ?” ፍርሃት ነው። እመኚኝ!! እመኚኝና ልብሽን ስጪኝ። አንድ ነገር ቃል እገባልሻለሁ። ልብሽን አልሰብርም
አልኳት። ዓይኗን ገርበብ አድርጋ ነበር የሰማችኝ ከመግለጧ በፊት አየኋት፡፡ ዓይኔ ከንፈሯ ላይ ቀረ። ውጤቱን ማሰብ
አልፈለግኩም።ወይም ምንም ቢሆን ግድ አልነበረኝም።
ከንፈሮቿን ሳምኳቸው። ለምን ያህል ሰከንድ እንደሆነ ባላውቅም
መልሳ ስማኛለች፡፡ እጇ በወገቤ ዙሪያ አልፏል። ይሄን ያሰብኩት ድንገት አቁማ ገፍታኝ ስትቆም እንጂ ስትስመኝ
ከጥፍጥናዋ ውጪ ማወቅ የቻልኩት ነገር አልነበረም።
“ኪሩ? ምንድነው የምታደርገው?" ጮኸችብኝ፡፡ ፈገግ አልኩ። ልቧን ስትሰማው ስማኛለች፡፡ መንገድ ላይ መሆናችን እንኳን አላሳሰባትም ነበር፡፡ አዕምሮዋን ስትሰማው ነው የገፋችኝ።
ባትነግረኝም የማትክደው ስሜት አላት። ፈገግታዬ አበሳጫት። ተናደደች።
"ኪሩ ሁለተኛ እንዲህ ብታደርግ እንጣላለን። የምሬን ነው!!"
አለች ድርጊቴ እንዳናደዳት ለመግለፅ እየጣረች።
"እሺ፡፡ ከዛሬ በኋላ ራስሽ ካልጠየቅሽኝ አላደርገውም::"
"ማለት?"
ኪሩቤል ሳመኝ ብለሽ አፍ አውጥተሽ ካልጠየቅሽኝ አልስምሽም።" አልኳት።
ወገኛ! ኪሩ እኔ አንተ እንደምታውቃቸው አይነት ሴቶች አይደለሁም።" አለች መንገድ እየጀመረች።
"አውቃለሁ!! ከነሱ የሚለይሽ ነገር ባይኖር ከነሱ የተለየ ስሜት
አትሰጪኝም ነበር።" መለስኩላት እርምጃዬን ከርሷ ጋር እያመጣጠንኩ።
'ለምን እኔን? ለምን? ደግሞስ ለምን አሁን? አንተ ማንም ሴት የምትደነግጥልህ ወንድ ነህ!"
"ማንም ሴት ደንግጣልኝ ይሆናል፡፡ ካንቺ ውጪ ያስደነገጠችኝ ሴት የለችም ለውጡ እንዴት አይታይሽም?" አልኳት።
ተለይታኝ ሄደችበልቤ። ተሸክሜያት ወደ ሱሴ ሄድኩ። በቀኖችህ ውስጥ ለምታደርገው ትግል ጥያቄው መሸነፍህ አይደለም።መዋጋትህ እንጂ ምክንያቱም ሳትታገል ሁሌም ውጤቱ የታወቀ ነው። ተሸናፊ ነህ። በትግልህ ውስጥ ውጤቱ ከሁለት አንዱ ነው። ማሸነፍ ወይም መሸነፍ!! ጥያቄው መዋጋትህ ላይሆን ይችላል የተዋጋህለት አላማ እንጂ። እሷ ናት። ምንንም ባልፍላት የሚገባት። እረፍት መውጣቷን ተከትሎ ናፍቆቷን መታገስ ከምችለው በላይ ነበረ። ስልኳ እረፍት ከወጣችበት ቀን ጀምሮ ዝግ ነው።ጭንቅላቴ የሚፈነዳ መሰለኝ፡፡
እቤቷ ላለመሄድ ከቁጥር በላይ ለሆነ ጊዜ አመነታሁኝ።
በስምንተኛው ቀን እሷን ሳላያት ባድር ትንፋሼ ቆሞ የማድር መሰለኝ።ከስራ ወጥቼ እቤቷ ሄድኩ:: በሩን ስትከፍትልኝ ምን እንደምላት፣ምን ለብሳ እንደማገኛት፣ ስታየኝ ምን እንደሚሰማት እያሰብኩ በሩን በስሱ ቆረቆርኩ ደገምኩት።ጨዋታ አቋርጦ እንደከፈተልኝ የሚያስታውቅ ሰው ያላለቀ ሳቁን እየቀጠለ በሩን ከፈተልኝ።
"አቤት?" አለኝ።
ሰምቼዋለሁ ዝም አልኩ፡፡ ደገመልኝ፡፡ ዝምታዬን ደገምኩለት።ስምሪት ከጀርባው ብቅ አለች። ምንም አይነት የፊት ሜክአፕ
ስትጠቀም አይቻት አላውቅም።ተቀባብታ ሌላ ሴት መስላለች፡፡ከከንፈሯ ውጪ ያልደመቀ የለም:: ለፓንትነት የቀረበ ቁምጣ እና ለጡት ማስያዣነት የቀረበ ሹራብ ለብሳለች። ፀጉሯ ቢመሳቀልም ተለቋል።እሱን አየሁት።በሲሊፐር ነው።
እንግድነት አይታይበትም።የከንፈሩ ጠርዝ ላይ አስተዋልኩ። ስምሪት ያስደነገጣት የኔ መምጣት ይሆን ወይም የመጣሁበት ሰዓት አላውቅም ደንግጣለች፡፡
"እንዴ? ኪሩቤል?" እየተንተባተበች ጨበጠችኝ፡፡
ሰውየው ለኔ ማሳወቅ የፈለገው ነገር ያለ መሰለኝ አቅፎ ወደ ራሱ አስጠግቶ ፀጉሯን ሳማት፡፡ እሷ በድርጊቱ ያፈረች መሰለኝ ዓይኔን ሸሸችው።
"ማሬ የስራ ባልደረባዬ ነው።" አለች ለሰውየው።ለኔ ደግሞ "የአርሴማ አባት ነው::" ተጨባበጥን።
“ኦው ፖሊስ ነህ? የሆሊውድ አክተር ነበር የመሰልከኝ፡፡ ሃሃሃ" ሰውየው መቀለዱ ነው።በቡጢ ዱልዱም አፍንጫውን ባጠፋለት ደስ እንደሚለኝ ቢያውቅ፡፡ በዚህ መሃል አርሴማ ዓይኗን እያሻሸች በአባቷና በእናቷ እግር መሃል ብቅ አለች። ስታየኝ ፈገግ ማለቷ ያስታወሰችኝ ስለመሰለኝ ደስ አለኝ። ልስማት
ስጠጋት ግን ሸሸችኝ፡፡
“ይቅርታ በማይሆን ሰዓት መጣሁ መሰለኝ። የስራ ጉዳይ እቤት ድረስ ይዤ መምጣት አልነበረብኝም::" መናገር ስለነበረብኝ አልኩኝ እንጂ እግሬ ከመሬቱ ጋር ያዛመደው ነገር ያለ ይመስል
አልተንቀሳቀስኩም።ሰውየው እንድገባ ጋበዘኝ፡፡ ለአፉ እንዳለው ያስታውቅበታል፡፡ተሰናብቻቸው እግሬን ከተተከለበት አንቀሳቅሼ በመጣሁበት አቅጣጫ መራሁት። አለመታደል ነው #ቀላውጦ_ማስመለስ ትል ነበር እናቴ፡፡ የምፈልገው ስለርሷ አለማስብ ነው። የማደርገው ግን ተቃራኒውን ነው
የጠራችው ሰውየው የስራ ባልደረባዋ መሆኔን እንዲያምናት ብቻ ነው? ድምፅዋ ውስጥ ለምን ፍርሃት ሰማሁ? ለምን ባለቤቴ ነው አላለችኝም የዛን
እለት አርሴማ
👍2
አባቷ እያለ በምን ስሌት እኔጋ ደወለች? የት ሄዶስ ነበር? ደጋግሜ እሷን ማሰቤን ለማቆም እታገላለሁ የሚገባኝ እሷን ማሰብ ስለማቆም እያሰብኩ እንኳን የማስበው እሷን መሆኑን ነው።
አንዳንዴ ራስህን ለማግኘት ራስህን ልትከፍል ትችላለህ።ለመጀመሪያ ጊዜ ስሜቴን በሱስ መበረዝ አላማረኝም። መታመም ፈለግኩ። ወደ ቤቴ ሄጄ ተጋደምኩኝ፡፡ ሁሉም ነገር ፀጥ አለብኝ።
በምድሪቷ ያሉ ፍጡሮች ሁሉ በሆነ መዓት አልቀው እኔና ቤቴ ብቻ አንድ የምድር ጠርዝ ላይ ተርፈን ከሆነ እንቅልፍ የነቃሁ
መሰለኝ፡፡ አመሻሹ ሲገፋ የመጠጣት ፍላጎቴ ታገለኝ፡፡ስልኬ ሲጠራ አላመንኩትም።ስምሪት ናት።
“እንደ ባለጌ ሴት ነው አይደል የምታስበኝ?" አለችኝ ስልኩን
አንስቼ ሄሎ ከማለቴ።በምን ምክንያት?” መለስኩላት።
ምን እንደምታስብ ይገባኛል።" አለችኝ በቀሰስተኛ ድምፅ።
“በፍፁም!! መገመት እንኳን አትችዪም። ስምሪት አጠገብሽ ሆኜ እንባሽን ከጉንጭሽ ላይ መጥረግ ነው ፍላጎቴ” ጥቂት ዝም አለች።
ማልቀሴን በምን አወቅክ?"
“ባለቤትሽስ? ወጥቶ ነው?"
አብሮኝ አይኖርም። አንዳንዴ ነው የሚመጣው፡፡” መለሰችልኝ፡፡መስማት የፈለግኩት ግን ባለቤቴ አይደለም' የሚለውን ነበር፡፡
"ልምጣ? እንዳይሽ ብቻ ነው::"
መምሸቱን እና ልጇ መተኛቷን ምክንያት ደርድራ እንዳልሄድ ከለከለችኝ፡፡ እውነቷን ነው መሽቷል፡፡ ወደርሷ መሄድ ግን
እየተጓዙ ማደር ቢሆን እንኳን ደስ እያለኝ አደርገው ነበር፡፡ ብዙ ጊዜ የሰቀልከው ተስፋጋ ለመድረስ መንጠራራት ተስፋውን
ከመጨበጥ በላይ ደስታ አለው:: ጉልበት እና የተስፋ ስንቅ ያጅቡታል። ስልኩን ዘግቼው ተጋደምኩ። የማስበው ምን
ከፍቷት እንዳለቀሰች ነው።የሰው ሚስት የመሆኗን ሀቅ ሆነ ብዬ ከሀሳቤ ላለመደመር እታገላለሁ።ላያት የመፈለጌን
እብደትም ችላ ልለው እፍጨረጨራለሁ። ብዙም ሳትቆይ መልሳ ደወለች።ግራ ተጋባሁ፡፡
“ሳልነግርህ ረስቼው የእናትህን አድራሻ ፍንጭ የሚሰጥ መረጃ ተገኝቷል።” በእርግጠኝነት ይሄንን ልትነግረኝ እንዳልደወለች ገብቶኛል፡፡
"እሺ በይኝ ልምጣና ልይሽ? አስር ደቂቃ ብቻ? ስለመረጃውም ትነግሪኛለሽ፡፡" ስላት በጣም ታሽታ ስታበቃ መለሰችልኝ።
"እሺ ግን እኔ ልምጣ! ተመልሶ ሊመጣብኝ ይችላል፡፡" አለችኝ፡፡
ቁጭ ብዬ እሷ እስክትደርስ መጠበቅ የምችል አልመስልህ አለኝ፡፡
“መሽቷል። እራሴ መጥቼ ይዤሽ እመለሳለሁ።ተዘጋጅተሽ ጠብቂኝ።" አልኳት።
የለበስኩትን ቱታ አልቀየርኩትም።እንዴት እንደደረስኩ አላውቀውም።እሷን የማግኘት ጉጉቴ ሰቅዞኝ ለብቻዬ ፈገግ
እያልኩ ነበር፡፡ ታክሲው ውስጥ ምን ያህል እንደተቀመጥኩም አላውቅም በሯ ላይ ስደርስ ደወልኩ፡፡ከመደንገጤ የተነሳ መመለስ ሁሉ ዳድቶኝ ነበር።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
አንዳንዴ ራስህን ለማግኘት ራስህን ልትከፍል ትችላለህ።ለመጀመሪያ ጊዜ ስሜቴን በሱስ መበረዝ አላማረኝም። መታመም ፈለግኩ። ወደ ቤቴ ሄጄ ተጋደምኩኝ፡፡ ሁሉም ነገር ፀጥ አለብኝ።
በምድሪቷ ያሉ ፍጡሮች ሁሉ በሆነ መዓት አልቀው እኔና ቤቴ ብቻ አንድ የምድር ጠርዝ ላይ ተርፈን ከሆነ እንቅልፍ የነቃሁ
መሰለኝ፡፡ አመሻሹ ሲገፋ የመጠጣት ፍላጎቴ ታገለኝ፡፡ስልኬ ሲጠራ አላመንኩትም።ስምሪት ናት።
“እንደ ባለጌ ሴት ነው አይደል የምታስበኝ?" አለችኝ ስልኩን
አንስቼ ሄሎ ከማለቴ።በምን ምክንያት?” መለስኩላት።
ምን እንደምታስብ ይገባኛል።" አለችኝ በቀሰስተኛ ድምፅ።
“በፍፁም!! መገመት እንኳን አትችዪም። ስምሪት አጠገብሽ ሆኜ እንባሽን ከጉንጭሽ ላይ መጥረግ ነው ፍላጎቴ” ጥቂት ዝም አለች።
ማልቀሴን በምን አወቅክ?"
“ባለቤትሽስ? ወጥቶ ነው?"
አብሮኝ አይኖርም። አንዳንዴ ነው የሚመጣው፡፡” መለሰችልኝ፡፡መስማት የፈለግኩት ግን ባለቤቴ አይደለም' የሚለውን ነበር፡፡
"ልምጣ? እንዳይሽ ብቻ ነው::"
መምሸቱን እና ልጇ መተኛቷን ምክንያት ደርድራ እንዳልሄድ ከለከለችኝ፡፡ እውነቷን ነው መሽቷል፡፡ ወደርሷ መሄድ ግን
እየተጓዙ ማደር ቢሆን እንኳን ደስ እያለኝ አደርገው ነበር፡፡ ብዙ ጊዜ የሰቀልከው ተስፋጋ ለመድረስ መንጠራራት ተስፋውን
ከመጨበጥ በላይ ደስታ አለው:: ጉልበት እና የተስፋ ስንቅ ያጅቡታል። ስልኩን ዘግቼው ተጋደምኩ። የማስበው ምን
ከፍቷት እንዳለቀሰች ነው።የሰው ሚስት የመሆኗን ሀቅ ሆነ ብዬ ከሀሳቤ ላለመደመር እታገላለሁ።ላያት የመፈለጌን
እብደትም ችላ ልለው እፍጨረጨራለሁ። ብዙም ሳትቆይ መልሳ ደወለች።ግራ ተጋባሁ፡፡
“ሳልነግርህ ረስቼው የእናትህን አድራሻ ፍንጭ የሚሰጥ መረጃ ተገኝቷል።” በእርግጠኝነት ይሄንን ልትነግረኝ እንዳልደወለች ገብቶኛል፡፡
"እሺ በይኝ ልምጣና ልይሽ? አስር ደቂቃ ብቻ? ስለመረጃውም ትነግሪኛለሽ፡፡" ስላት በጣም ታሽታ ስታበቃ መለሰችልኝ።
"እሺ ግን እኔ ልምጣ! ተመልሶ ሊመጣብኝ ይችላል፡፡" አለችኝ፡፡
ቁጭ ብዬ እሷ እስክትደርስ መጠበቅ የምችል አልመስልህ አለኝ፡፡
“መሽቷል። እራሴ መጥቼ ይዤሽ እመለሳለሁ።ተዘጋጅተሽ ጠብቂኝ።" አልኳት።
የለበስኩትን ቱታ አልቀየርኩትም።እንዴት እንደደረስኩ አላውቀውም።እሷን የማግኘት ጉጉቴ ሰቅዞኝ ለብቻዬ ፈገግ
እያልኩ ነበር፡፡ ታክሲው ውስጥ ምን ያህል እንደተቀመጥኩም አላውቅም በሯ ላይ ስደርስ ደወልኩ፡፡ከመደንገጤ የተነሳ መመለስ ሁሉ ዳድቶኝ ነበር።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 #Share ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍2