አትሮኖስ
286K subscribers
122 photos
3 videos
41 files
575 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
‹‹አንቺ በዚያ ምሽት.እዚያ ነበርሽ?"

‹‹ብኖር ባልኖር ምን ያርግልሻል…ብቻ ጁኒየርን ወዲያውኑ አገባኝ። ፣ ሁል ጊዜ የሚፈልገው ሰሎሜን መሆኑን ባውቅም ከሞተች በኃላ ግን ከሐዘኑ እንዲያገግም እንድረዳው እንደፈለገኝ አውቄ ነበር፡፡ከሀዘኑ ለማገገም ቢጠቀምብኝ ግድ አልነበረኝም። ለእሱ በሆነ ነገር ጠቃሚ ሆኖ መገኘት ፍላጎቴ ነበር ፡፡ ምግብ አበስልለታለው…ልብሱን አጥብለታለው…ሲፈልግ ደግሞ ወደ አልጋው ላይ እወጣለታለው፡፡ ከተጋባን በኋላም ለእኔ ታማኝ አልነበረም … ። ከቤት በምንወጣበት ጊዜ ሁሉም ሴቶች ወደ እሱ ሲሳብ እመለከት ነበር። የትኛውም ወንድ ያን የመሰለ ጠንካራ ፈተና መቋቋም ይችላል ?ብዬ እራሴን ጠየቅኩ ፡፡ከእኔ ጋር እንደተጋባ ቢቀጥል ኖሮ ፍቅረኛዎቹን ሁሉ በታገሥኳቸው ነበር።ነገር ግን ፍቺ ጠየቀኝ፣ መጀመሪያ ላይ እምቢ አልኩት፣ ቀጠለና እኔን መጉዳት መቀጠሉ ምቾት እንደነሳው ነገረኝ፣ ምንም አማራጭ ሳጣ ለእሱ የአእምሮ ሰላም ስል በፍቺው ተስማማው..
፣ ልቤ ተሰበረ፣ ቢሆንም ግን ስለምወደው የሚፈልገውን ሰጠሁት፣ እኔ እሱን እስከጥግ ድረስ በማፍቀሬ በሚደርስብኝ ስቃይ የምሞት ሁሉ ይመስለኝ ነበር…እንደማስበው እኔ የምረዳውን ያህል ማንም ሌላ ሴት እንደማትረዳው አውቃለው ››ንግግሯን ገታ አደረገችና አይኖቾን አለም ላይ አንከባለለቻቸው….ከዛ ቀጠለች"እና አሁንም ከጎኑ ቆሜ ከሴት ወደ ሴት ሲዘል እያየሁት ነው ፡፡ ሁል ጊዜ የሚፈልገውን ልሰጠው እፈልጋለሁ…ዛሬ ማታ እንኳን ሲጨፍር እና አንቺን ሲያሽኮረምም ለማየት ተገድጄያለው…ኦ አምላኬ!!!›› አለች እና አለቀሰች፣ ፊቷን ወደ ኮርኒሱ ቀና አደረገች…..አምላኳም ብሶቷን እንዲያዳምጥላት የፈለገች ትመስላለች፡፡

" አሁን አንቺም እሱን ልታጠፊው ትፈልጊያለሽ..እሱ ግን ከአንቺ ቁንጅና ባሻገር ያለውን ተንኮለኛ እቅድሽን ማየት አልቻለም››እጇን ዝቅ አድርጋ አለም ላይ ትኩር ብላ ተመለከተች

"አንቺ መርዝ ነሽ። ወ .ሪት አለም .. እኔ ዛሬ ማታ ስለአንቺ የተሰማኝ ስሜት ከሀያአምስት አመት በፊት እናትሽ ላይ ከሚሰማኝ ስሜት ጋር ተመሳሳይ ነው››በመካከላቸው ያለውን ርቀት አጥብባ ወደእሷ ተጠጋች እና

"ፈጽሞ ባትወለጂ እመኛለሁ...››አለቻትና መቀመጫዋን ለቃ በተቀመጠችበት ጥላት ሄደች፡፡

አለም ስርጉት ጥላት ከሄደች በኋላ እራሷን ለመሰብሰብ ያደረገችው ሙከራ ከንቱ ነበር። ፊቷ ገርጥቷል እና እየተንቀጠቀጠች ነው፡፡ ከበረንዳው ተነሳችና ወደአዳርሹ ገባች።" ጁኒየር እየጠበቃት ነበር።

"አሌክስ?ምንድነው ቆየሽ..?ልፈልግሽ መጥቼ ነበር..በረንዳው ላይ ከስርጉት ጋር እያወራችሁ ስለነበረ ልረብሻችሁ አልፈለኩም››
ዝም ብላ በተቋጠረ ፊት ታየው ጀመር፡፡ጨነቀው‹‹ ምንድነው ችግር አለ እንዴ?"

‹‹አሁን ወደቤቴ መሄድ እፈልጋለሁ." አለችው፡፡

"ታመሻል ? ምንድን ነው የተፈጠረው-"

"እባክዎ በመንገድ ላይ እንነጋገራለን››
.ጁኒየር ያለ ተጨማሪ ክርክር እጇን ይዞ ወደ ውጭ መራመድ ጀመረ.. ሆቴሉን ለቀው ወጡና ወደ ራሱ ቀይ ጃጓር ውስጥ አስገባት። መኪናዋ ተንቀሳቀሰች ፡፡ከአካባቢው የተወሰነ ከራቁ በኃላ

"እሺ ምን ሆናሻል?"ሲል ጠየቃት፡፡

"ስርጉት  ባለቤትህ እንደነበረች ለምን አልነገርከኝም?"

የሚነዳውን መኪና መሪ መቆጣጠር እስኪያቅተው ድረስ ደንግጦ አፈጠጠባትና አንገቱን አዙሮ መንገድ ላይ አተኩሮ። "

አልጠየቅሽም።"ሲል መለሰላት፡፡

አሁንም የሚንቀለቀል ንዴትና ቁጣ ላይ ነች…ምን ብላ እንደምትመልስለት አልገባትም፡፡የስርጉት የእሱ ባለቤት መሆን ብቻ ሳይሆን የዳኛው ሴት ልጅ መሆኗም ጭምር ነው ያበሸቃት፡፡ዳኛው ከሶስቱ የእናቷ ገዳይ ተጠራጣሪዎች ጋር በጋብቻ የተሳሰሩ የአንድ ግሩፕ አባሎች መሆናቸውን ስታስበው..የጀመረችው ነገር ምን ያህል አደገኛ እንደሆነ የበለጠ ገባት፡፡

"ግን ይህ ንዴት አስፈላጊ ነው?"ሲል ጁኒየር ጠየቀ።

"አላውቅም።"

" ነው የከነከነሽ ሌላ ጉዳይ አለ….?እስኪ ንገሪኝ?"
‹‹አይ ምንም የምነግርህ ጉዳይ የለም››

‹‹የእኔና የስርጉት ጋብቻ እኮ ከአንድ ዓመት ያነሰ ጊዜ ነው የቆየው። ከዛ በኃላ ጓደኛሞች ነን፡፡››
ንግግሩ የበለጠ አበሳጫት"

በፈጣሪ ጁኒዬር…ጓደኞሞች ነን ትላለህ እንዴ …?ሴትዬዋ እኮ አሁንም ከአንተ ጋር የጋለ ፍቅር ላይ ነች."

"በእኔ እና እሷ መካከል ያለው ዋናው  ችግርም  ይህ ነበር። ስርጉት ግትር  አፍቃሪ ነች
…ፋታ አትሰጥም… መተንፈስ ስላልቻልኩ ነው ልፈታት የተገደድኩት ››

"ፍቅሯ ቁንጣን ሆነብኝ እያልከኝ ነው …?በእውነት ግድ የለኝም ..ምንም አይነት ማብራሪያ እንድትሰጠኝ አልፈልግም››

"ታዲያ ቀድመሽ ለምን አነሳሽው?"

ምክንያቱም መፀዳጀ ክፍል ድረስ ተከትላ ስላፋጠጠችኝ… እና በዚህ ምርመራ የአባቷን ህይወት እያመሰቃቀልኩት እንደሆነ እና ከድርጊቴ ካልታቀብኩ እርምጃ እንደምትወስድብኝ ስለዛተችብኝ ነው››

"አሌክስ, ዳኛው አልቃሻ ነገር ነው፡፡ምን አልባት ስለ አንቺ ስርጉት ፊቷ አንድ አንድ አስከፊ ነገር ተናግሮ ለአንቺ አሉታዊ አመለካከት እንዲያድርባት ማድረጉን ለደቂቃ አልጠራጠርም. እሷ እንድታዝንለት ያደረገው ዘዴ ነው. አባትና ልጅ የተለየ አይነት ግንኙነት ነው ያላቸው፡ለተናገረችው ነገር ያን ያህል ትኩረት አትስጪው››

አለም ጁኒየር ላይ ያላት አመለካከት በጣም ነው የተዘበራረቀባት፡፡ ለሴት ያለው አመለካከት ፈጽሞ አልተመቻትም - ። ልክ ስርጉት እንደገለፀችው ዛሬ ማታ ከአንዷ ሴት ወደ ሌላ ሴት ሲዘዋወር ስትታዘበው ነበር። ወጣቱ እና በእድሜ የፀኑት ፣ ማራኪ እና ሽቅርቅሮች፣ ያገቡ እና ያላገቡ ፣ ከሁሉም ጋር ሲያሽካካ እና ሲጨዋት ነበር ። እሱ ህዝቡ እንደሚያገለግል የገበያ ማዕከል ሰራተኛ መስሎነው የተሰማት፣ ጁኒየር የሚያናግራቸው ሴቶች ሁሉ የሚፈልገውን ምላሽ እንደሚሰጡት እርግጠኛ እንደሆነ ታዝባለች ። ማንኛውንም የፈለጋትን ሴት ማሽኮርመም ለእሱ እንደ መተንፈስ ተፈጥሯዊ ነው። አንድ
ሰው ሃሳቡን በተሳሳተ መንገድ ተርጎሞ የስሜት ሥቃይ ሊደርስበት እንደሚችል እንኳን አያስብም..።ምናልባት እሷ ከስርጉት ጋር ባትወያይ ኖሮ እንደሌሎቹ ሴቶች በፈገግታው ወጥመድ ገብታ ተመሳሳይ ፈገግታ ትሰጠው ነበር ። አሁን በእሱ ላይ ተናድዳለች ፡፡

" ስርጉት ለዳኛው አባቷ ብቻ አይደለም የተከራከረችው።ካንተ ጋር ስለነበራት የትዳር ትዝታ እያነሳሳች ነበር ። የቀድሞ ጓደኛህ ልጅ መሆኔ ለእሷ እውነተኛ ፈተና እንደሆንኩ እንድታስብ ምክንያት ሆኗታል ። ያ የኔ ችግር አይደለም አይደል?››

"ምናልባት መሆን አለበት."ጠንከር ያለ ምላሽዋ አስገረመው።

" ተናደድሽብኝ አይደል?። ግን ለምን?"

"አላውቅም።" የንዴቷ ነበልባል አጭር እና ጣፋጭ ነበር። አሁን የድካም ስሜት ተሰማት።

"አዝናለሁ… ምናልባት ሁልጊዜ ትኩረት ለተነፈጋችው ሰዎች ስለምማረክ ሊሆን ይችላል ››

ቀኝ እጁን አነሳና የተራቆተ ጉልበቷ ላይ አሳረፈው ፡፡ አለም በዝግታ እጁን ከጉልበቷ ላይ አነሳችና በመካከላቸው ባለው የመኪናው የቆዳ መቀመጫ ላይ አሳረፈችው።

"ስርጉትን ለምን አገባሀት?"ስትል ጠየቀችው፡፡

"በእርግጥ መጠየቅ የምትፈልጊው ይህ ነው?" አለና መኪናውን ፍጥነት ጨምሮ ያግለበልበው ጀመር››

"አዎ።"

ፊቱን ወደ እርሷ አዞረና"

በወቅቱ መደረግ ያለበት ነገር ስለነበር››

"አትወዳትም።"

ዝም አለ..
"ከ ስርጉት ጋር ከማግባታችሁ በፊት ለረጅም ጊዜ ፍቅረኛሞች እንደሆናችሁ ነገረችኝ." "ፍቅረኛሞች አይደለንም አሌክስ። ግን ብዙ ጊዜ አወጣት ነበር።"

"ለምን ያህል ጊዜ?"
47👍6
"በግልጽ ማወቅ ትፈልጊያለሽ?"

"አዎ ንገረኝ››

"ባሰኘኝ ጊዜ ሁሉ››

"በዋነኛነት ከስርጉት  ጋር ፍቅር እየሰራህ  በምናብ ግን  የምትዘሙተው ከእናቴ ጋር እንደነበረ ታውቃለች?።››

"በኢየሱስ ስም..ንግግርሽ እንዴት ነው?››

‹‹እውነት ነው?"

"ሰሎሜ ሁልጊዜ ከገመዶ ጋር ነበረች…, ልክ እንደዚያ የህይወት እውነታ ነበር."

‹‹ ምንም እንኳን እሷ የቅርብ ጓደኛህ ብትሆንም ግን እሷን ትፈልጋት ነበር፣!" ዝም አለ

"ስርጉት አንድ ነገር ነግራኝ ነበር …እናቴን በተመለከተ"

"ምን?"

‹‹እናቴን ማግባት ፈልገህ ነበር።››

ለአንድ ሰከንድ ያህል አንገቱን አቀርቅሮ ከቆየ በኃላ “አዎ” ሲል መለሰ፡፡

"አግብታ እኔን ከወለደችን በኋላ ነው?"

"ከማግባቷ በፊትም ሆነ አግብታ ከወለደች በኃላ ላገባት እፈልግ ነበር."

ግራ መጋባቷን ሲያይ፣ “አንድ ወንድ ሰሎሜን አይቶ ለራሱ ሊያደርጋት መመኘቱ የሚቀር አይመስለኝም። ቆንጆ እና አስቂኝ ነበረች እና ለእሷ ልዩ እንደሆንሽ እንድታስቢ የምታደርግበት ጥበብ አላት ፤….የሆነ ነገር" ብሎ በቡጢ የመኪናውን ዳሽ ቦርድ በቁጭት ነረተው፡፡

"ከእናቴ ጋር ተኝተህ ታውቃለህ?"

"አይ … በጭራሽ ››

‹‹ሞክረህ አታውቅም? ››

‹‹ አይመስለኝም. በጭራሽ አልሞከርኩም. ቢያንስ ጠንከር ያለ ሙከራ ሞክሬ አላውቅም››

‹‹ በጣም የምትፈልጋት ከሆነ፣ለምን አልሞከርክም?"

"ምክንያቱም… ገመዶ ይገድለን ነበር."

በድንጋጤ ተመለከተችው።

‹‹የእውነት መሰለሽ እንዴ.. ለአገላለፅ ያህል ነው፡፡››

አለም ግን በማስተባበያው እርግጠኛ አልነበረችም፡፡ጣቶቹን በእሷ በኩል ወደ ላይ አንሸራትቶ አውራ ጣቱን አንገቷ ላይ አሳርፎ ደበሳት
"ይህ ..አስፈሪ ርዕሰ ጉዳይ ነው።››
‹‹እንለውጠው" በማለት በሹክሹክታ ተናገረ፣ ፡፡

እሷ ቤት ፊት ለፊት ደርሰው ስለነበረ መኪናውን አቁመው ወሪያቸውን ቀጠሉ፡፡

"ያለፈውን ለጥቂት ጊዜ ትተን ስለአሁኑ ብናስብ እንዴት ነው?›› ዓይኖቹ ፊቷ ላይ ተቅበዘበዙ

‹‹ስለአሁን ምን?››በለሆሳሳ ጠየቀችው፡፡

ድንገት " አሌክስ ካንቺ ጋር በፍቅር መጣመር እፈልጋለሁ።››አላት፡፡

ጥያቄው አስደናጋጭና ቅፅበታዊ ነው፡፡ለአፍታ ያህል አፍጥጣ ተመለከተችው፣ መናገር እስኪያቅታት ድረስ በጣም ደነገጠች።

"ቁምነገር አይደለም አይደል?"

"አረ ከምሬ ነው?"በማለት ፊቱን ወደእሷ አስጠጋ …ጭንቅላቱን በማዘንበል..ከንፈሮቹን በእሷ ከንፈሮች ላይ አሳረፈ…ምላሽ ባትሰጥም አልተቃወመችውም… ወደ ኋላ አፈገፈገ እና ግራ የተጋባ እይታን አያት።

"አይ።"

"ለምን አይሆንም?"

"እኔ ሳልነግርህ ታውቃዋለህ። ይህ ስህተት ነው።"

"ከዚህ በላይ ያበዱ ነገሮችን ሠርቻለሁ።" እጁን ወደ ሹራቧ ልኮ ለስላሳ ቲሸርቶን አልፎ ወደጡቶቾ ጣቶቹን ሰደደ…..

‹‹ይህ ፍፁም ስህተት ነው››

"አንድ ላይ ብንሆን ጥሩ ጥንድ ይወጣን ነበር ።"

"ጥሩ እንደሚሆን በፍፁም አናውቅም።››አዝጋሚ ግስጋሴውን በአይኑ እየተከታተለ አውራ ጣቱን በታችኛው ከንፈሯ ላይ አሳረፈ ።

"የማይሆን የለም።"

ራሱን ወደእሱ አስጠጋችና እና እንደገና በፍቅር ሳመችው፣ ከዛ የገቢናውን በራፍ ከፍታ ወረደች … በሩን መልሳ ዘጋችለትና

‹‹ደህና እደር›› አለችው፡፡ አገላለጹ አስደሳች ነበር። አለም በጣም ጨዋ ሆነችለት…እንደዚህም በመሆኗ እሷን ማግኘት የጊዜ ጉዳይ እንደሆነ እንደሚያስብ ታውቅ ነበር።

ቤቷን ከፍታ እንደገባች ነበር የዘጋችውን ሞባይል የከፈተችው…መልእክት ተልኳላት ነበር፡፡አያቷን ይከታተላት የነበረው ሀኪም ነው፡፡ይህንን መልእክት እንዳነበብሽ ደውይልኝ..አስቸኳይ  ነው››ይላል..በጣም  ከመደንገጧ  የተነሳ  ሰውነቷ  ተንዘፈዘፈ
…እንደምንም እራሷን አጠንክራ ደወለችለት፡፡

‹‹ሄሎ ዶክተር…አለም ነኝ››

‹‹እሺ አለም ..እንዴት ነሽ?››

‹‹ሰላም ነኝ ዶክተር..ደውለህልኝ ነበር መሰለኝ?››

‹‹አዎ በጣም አዝናለሁ፣ አያትሽ ከአንድ ሰዓት በፊት አርፋለች… ከገባችበት ኮማ ሳትነቃ ነው በዛው የሞተችው፡፡››

ስልኩን እንደዘጋች ወዲያው ነበር ሻንጣዋን ማዘጋጀት የጀመረችው፡፡ለማንም ሳትናገር መኪናዋን እራሷ እያሽከረከረች ለሊቱን ሙሉ ነድታ ሊነጋጋ ሲል አዲስ አበባ አያቷ የሞተችበት ሆስፒታል ደርሳ መኪናዋን አቆመች፡፡

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
56👍15
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

////

አለም የቢሮውን በራፍ አንኳኳች… የኩማንደሩን ‹ይግቡ› የሚል ሻካራ ቃል እስክትሰማ ድረስ ጠበቀች እና ወደውስጥ ገባች፡፡

"እንደምን አደርክ። ልታገኘኝ ስለፈቀድክ  አመሰግናለሁ።››በማለት ከጠረጴዛው ፊት ለፊት ባለው ወንበር ላይ ተቀመጠች ፡፡
ሳይጠይቃት አንድ ኩባያ ቡና ቀዳላትና ከፊት ለፊቷ አስቀመጠ።ስለቡናው አመሰገነችው። ተሸከርካሪ ወንበሩ ላይ ተቀመጦ፡

"ስለ አያትሽ አዝናለሁ ..አለም" አላት፡፡

"አመሰግናለሁ።"አለች፡፡

አለም የአያቷን የቀብር ሥነ ሥርዓት መፈፅምና ተያያዝ ጉዳዬችን መስመር ለማስያዝ ለአንድ ሳምንት አዲስአበባ ቆይታ ከመጣች ገና ሁለተኛ ቀኗ ነው ። በቀብሩ ላይ ጥቂት የድሮ ጓደኞቾ እና ከመቅዶኒያ የመጡ አያቷን በቅርበት የሚያውቁ ጥቂት ሰዎች ነበር የተገኙት፡፡… ከቀብር ሥነ ሥርዓቱ በኋላ አለም ወደአረጋዊ ማእከሉ ሄዳ የአያቷን እቃዎች መሰብሰብ ነበረባት…አብዛኛውን እቃዎች እዛው ለሚስፈልጋቸው ሰዎች በመስጠት ነበር ያስወገደችው፡፡
ከዛ ጥልቅ የሆነ ትካዜ ውስጥ ገባችው፡፡ ዳግመኛ ወደ ሻሸመኔ ከተማ መሄድ ይኑርባት ወይም እዛው አዲስአባ ትቅር ግራ ገብቷት ነበር፡፡አሁን አያቷ ሞተዋል….‹‹የእናትሽ ጋዳይ ነሽ››ብሎ እጣቱን የሚጠቁምባት ሰው የለም….ታዲያ ምን አሰቃያታል?፡፡በኋላ ግን ስታስበው እንደዛ ብታደርግ ፈፅሞ የመንፈስ እረፍት እንደማታገኝ ገባት …እንደውም ከበፊቱ በበለጠ እራሷን አጠንክራ ወደሻሸመኔ መመለስ እንዳለባት ወሰነች፡፡ ከህግ አንፃር፣ አሁንም ጉዳዩ በጣም ደካማ ነው…በዛም ምክንያት ፍርድ ቤት መቆም አልቻለችም። ከመካከላቸው የትኛው ለእናቷ ግድያ ተጠያቂ መሆን አለመሆኗቸውን ማወቅ አለባት። በዚህም ምክንያት ወደሻሸመኔ ተመልሳ መጣች።

ከደቂቃዎች ዝምታ በኃላ"እንደምትመለሺ እርግጠኛ አልነበርኩም" ብሎ በግልፅ ነገራት።

‹‹ተስፋ አልቆርጥም አልኩህ እኮ።››

‹‹ አዎ አስታውሳለሁ" አለ በብስጭት፡

"አዲስአበባ ከመሄድሽ በፊት የነጋዴዎች ማህበር አመታዊ ክብረ በአል ላይ ያሳለፍሽው ምሽት እንዴት ነበር?"በማለት ያልጠበቀችውን ጥያቄ ጠየቃት፡

በመገረም "እዛ ዝግጅት ላይ መሄዴን እንዴት አወቅክ?" ስትል ጠየቀችው፡፡ ዝም አላት፡፡

" ጁኒየር ነው የነገረህ?"

‹‹አይ።"

‹‹እና››

‹‹ምክትሌ በዛን ቀን ማታ …በአውራ ጎዳናው ላይ ከሱ ጋር በመኪናው ውስጥ አይቶሻል።ከፍጥነት በላይ ይነዳ ስለነበረ ቀልቡን ስቦት ነበር››

‹‹አዎ ነበርኩ…. ጁኒዬር ጋብዞኝ ሄጄ ነበር››

‹‹እንዴት ነው ጥሩ ጊዜ አሳለፍሽ?››

"ቆይ ስርጉት የጁኒየር ሚስት እንደነበረች ማንም ያልነገረኝ ለምንድን ነው?"

" አልጠየቅሽም።ደግሞስ ስላልተሳካ የድሮ ትዳር ማወቅ ለአንቺ ምን ይፈይድልሻል ?"

‹‹ሙሽራይቱ የዳኛው ልጅ ሆና መገኘቷ እንግዳ ነገር አይመስልህም? ።" "ይህ በፍፁም እንግዳ ነገር አይደለም."
"የአጋጣሚ ጉዳይ ነው እያልከኝ ነው?."

"አይ አይደለም:: ስርጉት ለመጀመሪያ ጊዜ ጂኒዬርን ካየችበት ቀን ጀምሮ በፍቅር ወይም በፍትወት ውስጥ ነበረች። ሁሉም ያንን ያውቅ ነበር። እሷም ምንም አይነት በደል በማንም ላይ አልፈፀመችም። ሰሎሜ ስትሞት. እድሏን ተጠቀመችበት።››

‹‹እንደዛ ነው የምታስበው››
"በግልፅ…ጁኒየር እንዲወዳት ማድረግ አልቻለችም።ምክንያቱም በየሄደበት እየተንሸራተተ የሚከፈተውን የሱን የሱሪ ዚፕ መዝጋት ለማንም ሴት ቢሆን የሚከብድ ፈታኝ ስራ ነበር።››

"ገመዶ፣ ጥድፊያው ምን ነበር? ጁኒየር ከስርጉት ጋር ፍቅር አልያዘውም ነበር። ታዲያ ለምን ተጋቡ?ነው ወይስ የቤተሰብ ግፊት ነበረባቸው?"

‹‹እነሱኑ ብትጠይቂያቸው አይሻልም?›› ከተቀመጠችበት ተነሳችና ወደ መስኮቱ አመራች፡፡

‹‹ያው አንተም ቤተሰብ ነህ ብዬ እኮ ነው ››

‹‹አዎ…ቤተሰቦቼ ናቸው..ሁል ጊዜ አብረውኝ ነበሩ …››

ወደ እሱ ዞር አለች፣ እሱ ግን ምንም እያያት አልነበረም። ‹‹አባቴ ሲሞት ከመላው የሻሸመኔ ኑዋሪ ለቀብር ሥነ ሥርዓቱ የመጡት አቶ ፍሰሀ እና ጁኒየር ብቻ ነበሩ ። ከቀብር በኃላ አቶ ፍሰሀ  ወደ ሥራ ተመለሰ። ጁኒየር ደግሞ ወደ ትምህርት ቤት ኄደ። እኔ ወደ ቤት ሄድኩ።ብዙም ሳይቆይ ሰሎሜ ወደ ቤቴ መጣች። ትምህርቷን አቋርጣ ነበር የመጣችው። አባቴን በህይወት እያለ ብጠላውም በመሞቱ ግን ብቸኝነት እንደሚሰማኝ ታውቅ ነበር። አልጋዬ ላይ አብረን ተኛን እና እስኪመሽ ድረስ እዚያ ቆየን። ወደ ቤቷ የሄደችው እናቷ እንደምትጨነቅ ስለሰጋች ነበር። ››
ንግግሩን ሲያቆም በክፍሉ ውስጥ ስሜታዊ ፀጥታ ሰፈነ። አለም ምንም እንቅስቃሴ ሳታደርግ በታሪኩ ተመስጣ .. በመስኮቱ አጠገብ ቆማ ነበር። በብቸኝነት የነበረውን ያንን ሚስኪን ወጣት አሰበችና ደረቷ ላይ ህመም ተሰማት።

"ከእናቴ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ፍቅር የያዘህ በዛን ቀን ነበር?"ስትል ጠየቀችው፡፡

በቀጥታ ወደእሷ ተመለከተ… እና ከወንበሩን ለቆ ወደ እሷ ቀረበ። "የፍቅር ጉዳይ ካነሳሽ… ያንቺ እንዴት ነው?"

‹‹የእኔ ምን?››በንዴት ጠየቀችው

"ከጂኒዬር ጋር…..?ማለቴ….››ሆነ ብሎ ንግግሩን አንጠልጥሎ ተወው

"አንተ ባለጌ ነህ"አለችው

"እንደሞከረ እርግጠኛ ነኝ። እሱ ሁልጊዜም ይሞክራል።››ሲል አከለበት፡፡

"ገሃነም ግባ።"

በእሷን በጁኒዬር መሀከል ስላለው ሁኔታ ለማወቅ ለምን አጥብቆ ፈለገ ?‹‹… አሁን ፊቱ ላይ የሚነበብበት ስሜት ምንድነው ?ምናልባትም ንቀት፣ ወይስ ቅናት….››አሰላሰለች፡፡

"ለምንድነው  ክረምት እናቴ ወደኮፈሌ ስትሄድ የፈቀድክላት…ወደዛ ባትሄድ ኖሮ ከአባቴ ጋር አትገናኝም ነበር….ከአንተ ጋር የነበራችሁ ፍቅርም እክል አያጋጥመውም ነበር››
"ምናልባት  የመልክአ  ምድር  ለውጥ  አስፈልጎት  ይሆናል….ወይንም  ደግሞ  ዘመዶቾ ስለናፈቋት…" ሲል በቁጭት ተናግሯል።

‹‹የቅርብ ጓደኛህ ምን ያህል ይወዳት እንደነበረ ታውቃለህ አይደል?።››
"በትምህርት ቤት ያሉ ሁሉም ወንዶች እናትሽን ያፈቅሯት እንደነበረ አውቃለው እና ደግሞ የከበርቴው ልጅ ከሆነው ጁኒዬር ጋር ስለ ፍቅር ጉዳይ አላወራም ነበር››.

"ጁኒየር እሷ ላይ ባለው ፍቅር ምን እንደተሰማው ታውቃለህ?"

‹‹ነገርኩሽ እኩ…ስለፍቅር ከእሱ ጋር አውርተን አናውቅም››

"እሷን ለማግኘት ምንም ነገር ቢሞክር ትገድለው እንደነበረ ነው የነገረኝ:: የእውነት ሁለቱም ቢከዱህ ትገድላቸው ነበር ?"

"እርግጠኛ ነኝ እንደዛ ያለሽ ንግግሩን ለማሳመር ፈልጎ ነው."አላት፡፡

"ጁኒየርም መልሼ ስጠይቀው የተናገረው ይህንኑ ነው፣ ግን አይመስለኝም" አለች
"ብዙ የሚቀሰቅሱ ስሜቶች ነበሩ። እርስ በርስ ያላችሁ ግንኙነት ተደራራቢ እና ውስብስብ ነው።"

"የምን ግንኙነቶች?"

"አንተ እና እናቴ ትዋደዳላችሁ፣ነገር ግን ሁለታችሁም ጁኒየርን ትወዱታላችሁ።››

"ምንድን ነው የምታወሪው? ከጁኒየር ጋር ፣አልወዳደርም."

"ምናልባት እያወቅክ ላይሆን ይችላል፣ ነገር ግን ሌሎች ሰዎች እርስ በእርሳችሁ ያወዳድራችኋል። እና ከመካከላችሁ የትኛው ነው ሁልጊዜ ወደላይ የሚወጣው? አንተ። ያ ያስጨንቅሀል?። ››
"ይሄ የአንቺ የስነ ልቦናህ ጫወታ ነው"

"የእኔ አስተያየት ብቻ አይደለም። ስርጉት በቀደም ይሄንኑ ነገር ነግራኛለች፡፡። ሰዎች ሁል ጊዜ ሁለታችሁን እንደሚያነፃፅሩና ጁኒየር ሁል ጊዜ በሁለተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ነግራኛለች።"
43👍6
"ሰዎች ምን እንደሚያስቡ መርዳትም መቆጣጠርም አልችልም."
"ጁኒየር የሰሎሜ ፍቅረኛ መሆን ፈልጎ ነበር ነገር ግን አንተን ፈርቶ ተወው ››

በመሀከላቸው ረጅም ጸጥታ ሰፈነ፡፡"አለም ጥሩ እየሞከርሽ ነው፣ ግን ከእኔ ለምርመራሽ የሚጠቅምሽ ምንም ነገር አታገኚም " አላት።
"እሺ ፍቅረኛዋ አልነበርክም? አሁን ነገሩን ማድበስበስ ምን ለውጥ ያመጣል?" የፀሐይ ብርሃን እያረፈባት ያለውን ከንፈሯን እንዲሰማት ፈለገች ....ወደእሷ ተጠጋ …በድንገት፣ እጁን  ጀርባ ላይ በማሳረፍ ወደ እሱ ጎትቶ፣ ፊቷን  በቀጥታ ወደፊቱ አዞረና ዓይኖቹን ዓይኖቿ ውስጥ ተከላቸው፡፡

"የአንቺ ቆንጆ ልዕልት… እኔን ለመፈታተን አትሞክሪ…እኔ የወንጀል ጉዳዮችን በመከታተል እና ፍርድ ቤት በመመላለስ አስራ ስምንት አመታትን አሳልፌለሁ እና በዛ ላይ እንደምታይኝ በተፈጥሮ ብልህ ነኝ ፡፡››እጁን ይበልጥ አጠበቃና ከራሱ ጋር ለጠፋት፡፡የ ትንፋሿ ሙቀት ተሰማው እና በፍጥነት ወደ ፊቷ ተጠጋ። "በእኔና በጁኒየር መካከል ስንጥቅ ለማግኘት አትሞክሪ.. ሰማሽ? ››ዓይኖቹ ጠበቡ። "እናትሽ በሁለቱ ጫፎች መሃል ላይ የመጫወት መጥፎ ልማድ ነበራት ። እንደእዚህ አይነት ጫወታ አግባብ እንዳልሆነ ትምህርት ከማግኘቷ በፊት ገደሏት። እንደዚህ አይነት ነገር በአንቺ ላይ ከመድረስ በፊት ብትማሪ ጥሩ ነው።"

በንዴት መነጨቀችውና ከእቅፉ ወጥታ ቢሮውን ለቃ ወጣች…በፍርድ ቤቱ ህንጻ ላይ ወደአለው የራሷ ቢሮ ተመልሳ ያልተረጋጉ ሀሳቦችን እያሰላሰለች እና ነገሮችን በመቀጣጠል የተወሰኑ መላምቶችን እየገመገመች ቆየች። ግን አንድ ሀሳብ እሷን እያስጨነቃት ነው። በእናቷ ሞት እና በጁኒየር ፈጣን ጋብቻ መካከል የሆነ ግንኙነት ያለ መስሎ እየተሰማት ነው፡፡የዳኛው ሴት ልጅ ስርጉትን በቀላሉ ከአእምሮዋ ልታወጣት አልቻለችም፡፡እስካሁን ከመረመረቻቸው ሰዎች ሁሉ እናቷን ለመግደል በቂ የሆነ ጥላቻ እና ምክንያት ያላት እሷ ሆና ነው ያገኘችው፡፡ከመሞቷም ቢያንስ ለጊዜው ትልቁን ትርፍ ያገኘችው እሷ ነች፡፡ወዲያው ጂኒዬርን አሳምና ልታገባው ችላለች፡፡እና ከጀርባ አድብታ የገደለቻት ወይም ያስገደለቻት እሷ ብትሆንስ?በአእምሮዋ ያሰላሰለችውን በጠቅላላ በማስታወሻ ደብተሯ ላይ አሰፈረች፡፡

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍3418
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_አንድ


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///

ገመዶ እኩለ ለሊት ላይ ስልኩ ጮኸ….

"ምንድን ነው ነገሩ" በማለት እየተነጫነጨ በተኛበት እጁን ዘረጋና ስልኩን ከኮመዲኖ ላይ አንስቶ ጆሮው ላይ ለጠፈና ‹‹ሄሎ››አለ፡፡

‹‹ኮማንደር መስማት አለብህ ብዬ ነው…ድንገተኛ ነገር ተከስቷል."ምክትሉ ነበር፡፡ ከመኝታው ተነሳና አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠ፡፡

"…ምንድነው የተፈጠረው?"

"ከእርባታ. ቦታው …ማለቴ የቤተሰቦችህ እርባታ ቦታ፣ከዛ ነው የተደወለልን"አለው…

ከአልጋው ወርዶ ጂንስ ሱሪውን መልበስ ጀምሮ ነበር፡፡ጭንቅላቱ የፍርሀት ቅዝቃዜ ሲፈስ ታወቀው፡፡

"ምን አይነት ድንገተኛ አደጋ ነው?"
‹‹ገና አልተረጋገጠም..ኃይል ወደእዛው ልከናል፡፡›› ያልተቆለፈ ሸሚዙን ከቆለፈ በኋላ ቆሞ ጫማውን አደረገ፡፡

‹‹በቃ ቶሎ አጣርተህ ደውልልኝ…ወደእዛው እሄዳለው፣ይሄው እየወጣሁ ነው… ››ስልኩን ዘጋና ኮቱንና ኮፍያውን አድርጎ ወደ ኮሪደሩ ሮጠ።
/////

አለም በከባድ እንቅልፍ ውስጥ ነበረች፣ ለዚህም ነው የበሯን መንኳኳት በህልሟ መስሎ የተሰማት…።ህልም ውስጥ ነበረች….በመጨረሻ ተከታታይ የሆነው የጥሪ ድምፅ ከእንቅልፏ ቀስቅሷት።

"ተነሺ እና በሩን ክፈቺ."በቁጣ እየጮኸባት ነው፣ ቁጭ አለችና አልጋው ዳር ያለውን መብራት አበራችው… መብራቱ ሲበራ …. ብርሃኑ ዓይኗን አጭበረበራት።

"ገመዶ ነኝ… ክፈቺ?" ጮኸ ። ዝም አለችው፡፡

"በአስር ሰከንድ ውስጥ ካልተነሳህሽ በሩን ሰብረዋለው››

የግድግዳውን ሰዓት ተመለከተች። ከምሽቱ ስምንት ሰዓት ገደማ ነበር።

‹‹ኩማንደሩ ወይ ሰክሯል ወይም አብዷል።››ስትል አሰበች፡፡ ያም ሆነ ይህ አሁን ባለበት ሁኔታ በሯን ልትከፍትለት አልፈለገችም።

"ምን ፈለክ?"

ከእሱ መልስ ስትጠብቅ በራፉ ላይ ፈንጅ የተጣለበት ይመስል ጎጎጎጎ አለና ተከፈተ….ተንደረደረና መኝታ ቤቷ ገባ፡፡በድንጋጤ እየተንቀጠቀጠች አልጋዋ ላይ ቆመች "ምን እየሰራህ ነው?"ብላ ጮኸችበት በቆመችበት አልጋ ልብሱን እየሰበሰበች እርቃኗን ለመሸፈን እየጣረች ነው››

"አንቺን ለማግኘት ነው የመጣሁ ‹‹
ከአልጋው ላይ ጎተተና ወለሉ ላይ አቆማት፣የተጠቀለለችበትን አልጋ ልብስ ከላዬ ላይ ገፎ ወረወረው፣እርቃኗን በፓንት ብቻ ፊት ለፊቱ ቆመች፣ምን ሊያደርጋት እንደሆነ መገመት ሁሉ አልቻለችም፡፡

"ኩማንደር በሬን ገንጥለህ መኝታ ቤቴ ለመግባትህ በቂ ምክንያት እንዳለህ ተስፋ አደርጋለሁ።"

"ማብራሪያ አለኝ።" አለና መሳቢያውን ከፈተ እና ውስጡ ያሉትን ልብሶች ማተረማመስ ጀመረ።

"ንገረኝ ምን እየፈለክ ነው?."አለችና እርቃኗን ወደእሱ ሄዳ ሚያተራምሰውን  የቁምሳጥን በራፍ በዳሌዋ ገፋችና ዘጋችበት ፡፡

"ምን ፈልገህ ነው?"ዳግመኛ ጠየቀችው፡፡
"ልብስ። እንደዚህ እርቃንሽን  መውጣት ካልመረጥሽ በስተቀር  ምትለብሺው ልብስ ያስፈልግሻል››

‹‹ወደየትም አልሄድም››

" ጂንስሽ የት ነው ያለው?›› በ ወፍራም ድምፁ ጠየቀ ። "የትም አልሄድም። ስንት ሰዓት እንደሆነ ታውቃለህ?››

ድንገት ቀና ሲል ከአልጋው አጠገብ ባለው ግድግዳ ልብሷ ተሰቅሎ አየው፡፡ ጂንሱን ከተሰቀለበት ላይ አወረደና ወረወረላት፣ መያዝ ስላልቻለች ወደ ወለሉ ወደቀ።
ከጫማዋቾ ውስጥ አንዱን መረጠና ወደእግሯቾ አቀረበላት፡፡ ዝም ብላ ፈዛ ታየው ጀመር፡፡ "እሺ.. እንዳለብስሽ ትፈልጊያለሽ?"

እሱን ለማስቆጣት ምን እንዳደረገች መገመት አልቻለችም። እርቃኗን እሱ ፊት ቆማ መከራከሩ ስለደከማት ጆንሱን አነሳችና አጠለቀች ፡፡ከላይ ሹራብ ለበሰች….ከኮመዲኖ መሳቢያ ውስጥ አንድ ካልሲ አወጣችና አራግፋ አጠለቀችና ጫማዋን አደረገች፡፡ በመጨረሻም ዞር ብላ አየችው።

"እሺ ይሄው ልብስ ለብሻለሁ …አሁን ምን እየተካሄደ እንደሆነ ንገረኝ ?"

"እየሄድን  እነግርሻለው  ››አለና  እጆቿን  በመያዝ  እየጎተተ  ይዞት  ወጣ  ፡፡በንዴት እየተንቀጠቀጠች ነበር።

‹‹እንዲህ እንድታደርገኝ ማን ነው የፈቀደልህ?››

"አንገትሽን መስበር አለብኝ…..አላደረገውም››በማለት ወደእሷ ተጠጋና ከንፈሯን ሳማት።ያለተቃውሞ ተሳመችለት፡፡ምላሱን ወደ አፏ ውስጥ አስገባ። በዚህ ጊዜ በቁጣ ስሜት መነጨቀችውና እራሷን አላቀቀች፡፡

ኮትዋን ከሳሎን በራፍ አካባቢ ካለው ማንጠልጠያ አነሳችና ያዘች፡፡ ከቤት ይዞት ወጣ " በሩስ?"ብላ ጠየቀችው ።
"የሚጠግን ሰው እልካለሁ።"

"በዚህ ለሊት?"

"በፈጣሪ … በሩን እርሺው..በአካባቢው ቤትሽን በንቃት የሚጠብቁ ፖሊሶች አሉ" ብሎ ጮኸ።

‹‹የሚጠብቁ ነው ሚሰልሉኝ?››

እጇን ጨምድዶ እንደያዛት ስትጠብቀው ወደነበረ ታክሲ ውስጥ ይዞት ገባ፡፡

"በፈጣሪ ገመዶ…ምን እየተፈጠረ ነው……?ነው ወይስ እያሰርከኝ ነው?››

‹‹እያሰርከኝ ..አንቺን……?ምነው ወንጀል ሰርተሸል እንዴ?›› ፡፡

‹‹እና ምንድነው ንገረኛ….?ወደየት እንደምሄድና ለምን እንደምሄድ የማወቅ መብት አለኝ›› ።

"የእርባታ ቦታው እየተቃጠለ ነው."

‹‹የእርባታ ቦታው.?.የነጁኒዬር?››

‹‹አዎ››

‹‹ወይ..ፈረሶችህ ተረፉ?››

ፈረሶቹን ምን ያህል ይወዳቸውና በምን ያህል መጠን ይንከባከባቸው እንደነበረ ስለምታውቅ ነው ቀድማ ስለፈረሶቹ የጠየቀችው፡፡

‹‹አላውቅም…የወደመውንና የተረፈውን ስንደርስ ነው የምናውቀው፡፡››
////
ሲደርሱ እሳቱ ከፈረሶቹ ጋጣ አካባቢ እየተንቀለቀለ ነው…በአንድ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሚገኘው የእንጨት ፋብሪካው ከአደጋ ውጭ ነው፡፡ቢሆንም በንፋስ ታግዞ ወይም በሆነ ምክንያት እሳቱ እዛ ቢደርስ ከፍተኛ ውድመት እንደሚያስከትል የታወቀ ነው፡፡

እንደደረሱ መኪናዋ ስትቆም ኩማንደሩ ከመኪናው ወረደና ወደእሳቱ አቅጣጫ ተንቀሳቀሰ…አለም ከኋላው ተከተለችው፡፡ከአንዱ የፈረስ ጋጣ ጭስ ሲትጎለጎል ይታያል…አለም ሆዷ ተገለባበጠባት። የእሳት አደጋ መከላከያ ሰራተኞች፣ የደንብ ልብሳቸውን ለብሰው እሳቱን ለመቆጣጠር እየሞከሩ ነበር።ብዛት ያላቸው የእርባታው ሰራተኞችና የአካባቢው ኑዋሪዎች ቅጠለም አፈርም እየተጠቀሙ እሳቱ እንዳይዛመት ለመቆጣጠር እየተረባረቡ ነው፡፡
አንድ ሰው ወደኩማንደሩ ቀርቦ"በጣም ብዙ ጉዳት ከማድረሱ በፊት ደርሰውበታል" ሲል ነገረው፡፡

‹‹ሰውስ አልተጎዳም?››

‹‹አንድ የተጎዳ ሰው አለ…››የሚል ድምፅ ሰማ፡፡

"ማንው የተጎድቷል?"

‹‹በጣም አሰቃቂ ትዕይንት ነበር።ከፈረስ ተንከባካቢዎች አንዱ ነው… በቂ አየር ወደ ሳምባዋ መሳብ አልቻለችም። ፈረሶችን ለማዳን ሲሯሯት አንድ እግሩም ተሰብሯል››

በዛ ቅፅበት አንድ ፈረስ እየጮኸ ነበር፣ በግልጽ ህመም ላይ እንዳለ ያስታውቃል። አለም እስካሁን ሰምታ የማያውቀው እጅግ አሳቃቂ ድምፅ ነበር የሰማችው። ገመዶ በፍጥነት ወደእዛው አመራ…ከኃላው ተከተለችው….የአቶ ፍሰሀ ቤተሰቦች በጠቅላላ በለሊት ቢጃማቸው በአካባቢው ነበሩ ፡፡መኖሪያ ቤታቸው ከእርባታው ድርጅት ብዙም ሰላማይርቅ እንደሰሙ በእግራቸው ነው ሮጠው ወዲያው ነው የደረሱት፡፡ ሳራ እያለቀሰች ነበር። ፍሰሀ

እራሱን ተቆጣጥሮ በፅናት ቆሞ ይታያል…ጁኒዬር እናቱን አቅፎ ያፅናናል፡፡ ገመዶ ወደ ጎን ገፋቸው እና እሳቱ ጠፍቶ ጭሱ ብቻ ከሚታይበት ጋጣ ውስጥ ገባ ፡፡
49👍4🔥1
" የሚወደው ፈረሱ የጋጣው ወላል መሀል ተዘርሮ እየተንፈራፈረ ነው፣ነፍሱ እንድትወጣ በመፈለግ የሚያሰማው የሚያሰቀጥጥ ጩኸት የሰው ጣር ነው የሚመስለው። አለም ባለችበት ቆማ ወደውስጥ ተንጠራርታ ፈረሱን አየችው ..ባለፈው ከኩማንደሩ ጀርባ ላይ ተለጥፋ የጋለበችበት ፈረስ ነው። ምን ያህል ይወደው እንደነበረ በዛን ቀን በደንብ መረዳት ችላለች፡፡
አንድ ሰው ገመዶን ተከትሎ ወደ ጋጣ ውስጥ ገብቷል "ለእሱ ማድረግ የምችለው ምንም ነገር የለም፣››አለው

"ገመዶ ሰውዬው ሲናገር ዝም ብሎ ተመለከተው። የሳራ ልቅሶ ጨመረ። ፊቷን በፎጣዋ ሸፈነች።

"እናቴ እባክሽ ወደ ቤት ልመልስሽ።››አላት ጁኒዬር…ጁኒየር እጁን ወገቧ ላይ አድርጎ ቀስ ብሎ ወደ መሀል መንገድ ይዞት ይሄድ ጀመር። ድንገት ሳራ ዞር ስትል አለምን ተመለከተቻት…ከዛ ከፍ ባለ ድምፅ አወጣች እና ሌባ ጣቷን ወደእሷ እየጠቁመች።

"አንቺ ነሽ ይህን ያደረግሽው።…አንቺ ነሽ››ስትል አንባረቀችባት፡፡

አለም ደነገጠችም..ግራ ገባትም "እኔ?"

" አዎ…ጥፋቱ ያንቺ ነው፣ አንቺ ቂመኛ ሴት ነሽ!"

"እማዬ…ተይ እንጂ" አለ ጁኒየር፣ ፡፡እንዳቀፋት ከአከባቢው ይዞት ሄደ ፡፡አለም ንዴት እና እልህ እየተናነቃት እይታዋን ወደጋጣው መለሰች፡እየተሰቃየ ያለውን እንስሳ ተመለከተች። ከገመዶ ጋር ያለው ሰው የእንስሳት ዶክተር እንደሆነ ገባት፡፡

" መርፌ ወግቼው ነበር …መድሀኒቱ እየሰራ አይመስለኝም..በቃጠሎ በጣም ስለተጎዳ መኖር ቢችል እኳን ከአሁን ወዲያ የምታውቀውን አይነት ፈረስ አይሆንልህም››በማለት ለገመዶ አስረዳው፡፡

ሁሉም ከፈረሱ የሚመወጣውን አሳዛኝ ድምፆ እያዳመጡ ለአፍታ ዝም አሉ። በመጨረሻ ፍሰሀ

"እናመሰግናለን ዶ/ር ፣ የምትችለውን ሁሉ እንዳደረክ እናውቃለን።"አለው

"ይቅርታ …የሚረዳው ከሆነ ወደኪሊኒክ ሄጂ አንድ መድሀኒት አለ ….እሱን አምጥቼ ልወጋው እችላለሁ…ቢያንስ ህይወቱን ባያተርፍለትም ስቃዬን ይቀንስለታል››

"አይ… ያን ያህል ጊዜ እየተሰቃየ እንዲጠብቀው አልፈቅድለትም.
"አለ ገመዶ

"አስር ደቂቃ አይፈጅብኝም።"ዶ/ሩ መለሰ፡

"ግድ የለም…አያስፈልግም…ባይሆን ሌሎች የተጎዱ እንስሳቶች ካሉ እነሱን እይልን….እሱን ለእኔ ተውልኝ›› ሲል ትግስት የለሽ በሆነ ቃላት ተናገረ …ዶ/ሩ እቃውን ሰበሰበና ከአካባቢው ለቆ ሔደ፡፡ ገመዶ ፈረሱ ስር ተንበረከከና ይዳብሰው ጀመር›‹‹ ደህና ትሆናለህ ፣ የእኔ ጀግና
?" በማለት ያባብለው ጀመር….ከዛ ወደአቶ ፍሰሀ ቀና አለና‹‹ጋሼ አንተ ወደቤት ሄድ…እኔ አስተካክለዋለው››አለው

"አዛውንቱ ለመጨቃጨቅ የተዘጋጁ ቢመስልም በመጨረሻ ግን በኩማንደሩ ሀሳብ በመስማማት ዘወር አሉ። አለምን ጠንከር ያለ ትርጉሙ የማይገባ እይታ ተመለከታት እና
፣ ምንም ሳይናገራት በአጠገቧ አልፎ ከአካባቢው ለቆ ሄደ፡፡ ገመዶ በወለሉ ላይ ከፈረሱ ጎን ተንበርክኮ ሲተክዝ ስትመለከት ማልቀስ አማራት፡፡ ፈረሱም ሰውዬውም አንጀቷን በሏት፡፡

"ጥሩ ፈረስ ነበርክ ምርጥ" መዳበሱን ቀጠለ፡፡"ያለህን ሁሉ ሰጥተኸናል.. ከዛም በላይ ›› ስንብት የሚመስል ቃላቷችን አዝጎደጎደ ።ገመዶ ቀስ ብሎ እጁን ወደታች ላከና በጎኑ የሻጠውን ሽጉጥ አወጣ… ካዝናውን ከፈተና ጥይት መኖሩን አረጋግጦ መልሶ አስተካከለው…..አለም ምን ሊያደርግ ነው ብላ በድንጋጤ እየተመለከተችው ነው፡፡ ከዛ ሽጉጡን ፈረሱ ጭንቅላት ላይ አስጠግቶ ደቀነ…

"ገመዶ፣ አይ፣ አታድርገውም። ሌላ ሰው ያድርገው።"ተንደረደረችና ወደውስጥ ገብታ እጅን ያዘችው፡፡

እስከዛሬ ገመዶን ስታውቀው ፊቷ ላይ እንዲህ ያለ የገዳይ ሰው እይታ አይታበት አታውቅም። ዓይኖቹ እንባ ማቅረራቸው ብቻ ሳይሆን ጥላቻም ማጋታቸውን በግልፅ ማየት ይቻላል፡፡ ሽጉጡን ልትቀማው ሞከረች ። ታገለችው። በፈርጣማ ግራ እጁ አንገቷን ፈጥርቆ ያዛትና በቀኝ እጁ የያዘውን ሽጉጡን በፈረሱ ሁለት አይኖች መካከል ባለው ግንባሩ ላይ አስተካክሎ አነጣጠረ እና ምላጩን ሳበው ….ክፍሉ በተከታታይ ተኩስ ተደበላለቀ….እሷ በድንጋጤ ጮኸች። አካባቢ የነበሩ ሌሎች ፈረሶች እና ከብቶች በፍርሃት በረገጉ

ከውጪ ያሉ ሰዎች ሲጮቾሁ ተሰማ ፣ እና በርካታ የእሳት አደጋ ተከላካዮች የተኩሱን ምክንያት ለማረጋገጥ ወደአካባቢው ሮጡ።ገመዶን እና አለምን ከጋጣው አስወጣችው።

በንዴት በሚንቀጠቀጥ ድምፅ‹‹በሰው ህይወት ውስጥ ጣልቃ መግባትሽን አቁሚ…በቃ አቁሚ››ጮኸባት፡፡

‹‹አንተም በጣም የምትወዳቸው ነገሮችንም ጭምር ማጥፋትህን አቁም››ብላ በተመሳሳይ ቶን ጮኸችነት፡፡

‹‹ለምወዳቻው የሚበጃቸውን ነገር ከማድረግ ወደኃላ አልልም….ነፍሴን ምትሰቃይ ቢሆንም እንኳን ግድ የለኝም ››

ስለፈረሱ ብቻ ሳይሆን ስለእናቷም እያወራ እንደሆነ ገባትና በፍርሀት ተንቀተቀጠች፡፡እሳቱ ሙሉ በሙሉ መጥፋቱን የእሳት አደጋ ኃላፊው አረጋገጠ፡፡ አቶ ፍሰሀ ፤ገመዶና አለም ተከታትለው እዛው አካባቢ ወደሚገኘው የአቶፍሰሀ ቤት ሄዱ፡፡ሲደርሱ ጁኒዬር ሳሎን ቁጭ ብሎ እየተከዘ ነበር፡፡

ሳሎን ተከታትለው እንደገቡ "ሳራ እንዴት ነች?"ሲል አቶ ፍሰሀ ጠየቀው፡፡

" እንድትረጋጋ አድርጌታለው….አሁን መድሀኒት ወስዳ ተኝታለች."ሲል ጁኒየር መለሰ።

አቶ ፍሰሀ "እስኪነጋ ድረስ ምንም ማድረግ ስለማንችል ወደ መኝታዬ ልሂድ …. አመሰግናለሁ ገመዶ፣ ባንተ ባይሆን ኪሳራችን ከዚህም በጣም የከፋ ይሆን ነበር፡፡ ››

‹‹ጋሼ..እናንተ እኮ ቤተሰቦቼ ናችሁ ….የወደመው የእኔም ንብረት ጭምር ነው››

‹‹አውቃለው…..ስለፈረሶችህ አዝናለው…ግን ከዚህ በፊት ደጋግመን ሊጥሉን ያሉትን ሰዎች አሸንፈን እንደተነሳን ከዚህኛውም ውድቀት በድል እንነሳለን››

‹‹አዎ እንነሳለን››ሲል በሀሳቡ ተስማማ፡፡

ጁኒየር እየተንቀጠቀጠች ያለችው አለም ዞር ብሎ አያት"አሌክሶ …አሁን ወደ ቤትሽ እንዳደርስሽ ትፈልጊያለሽ አለም? ››ሲል በሀዘኔታ ጠየቃት፡፡

"የስራዋን ውጤት እንድታይ ፈልጌ ነበር ያመጣዋት " አለ ገመዶ ጣልቃ ገብቶ ።

"ከዚህ እሳት ጋር ምንም ግንኙነት የለኝም!"በንዴት እየተንዘረዘረች አለቀሰች።

"ምናልባት በቀጥታ ላይኖርሽ ይችላል" ሲል ፍሰሀ ገመዶን ደግፎ በቁጣ መለሰላት፣ "ነገር ግን ይህ በእኛ ላይ የከፈትሽው የሞኝ ምርመራሽ ተስፋ ቆርጠው ትተውን የነበሩ ጠላቶቻችን እንዲነቃቁና ብርታት እንዲያገኙ ምክንያት ሆኖቸዋል፡፡ ››

"ነገሮችን በዚህ መንገድ  ካየኸው ይቅርታ ጋሽ ፍሰሀ "አየሩ በውጥረት ተሞላ ።
በመጨረሻም ጁኒየር ወደ ፊት ሄዶ ክንዷን ያዘና

" ነይ ላደርስሽ።" አላት፡፡

"እኔ እመለሳታለሁ" ገመዶ በቁጣ አንቧረቀበት።

"የራሳችሁ ጉዳይ..ለማንኛውም እኔ ሄጄለሁ።" ጁኒዬር በንዴት ለመሄድ ተንቀሳቀሰ

"በቃ ይዘሀት ሂድ።" ገመዶ ነበር

"አንተ ነህ ያመጣኋት አይደል? የአንተ ኃላፊነት ነች" በማለት ክፍሉን ሙሉ በሙሉ ለቆ ወጣ፡

ፈገግታ የሌለው ፍሰሀ ልጁን ተከትሎ ወጣ። ገመዶ እና አለም ብቻቸውን ቀሩ

"ነይ" ብሎ ወደውጭ ተራመደ….።ተከተለችው እና በጭንቀት ምክትሉ ይዞት ወደነበረው የቢሮ መኪና ውስጥ ተከትላው ገባች።በዝምታ አካባቢውን ለቀው ወደእሷ ቤት አቅጣጫ መጓዝ ጀመሩ…. አስፈሪውን ዝምታ ለመስበር የሆነ ነገር ማለት ፈለገች፣ ነገር ግን አንዲት ቃል መናገር አልቻለችም። ገመዶ እሷን ለማናገር ፍቃደኛ የሆነ አይመስልም ፡፡

በመጨረሻም በደረቷ አካባቢ እየጨመረ የመጣውን የጭንቀት ቋጠሮ ስላፈናት ለመናገር ወሰነች
36👍2🥰1
"ዛሬ ምሽት ከተፈጠረው ነገር ጋር ምንም ግንኙነት የለኝም" አለችው።አንገቱን ዞር አደረገና ግራ በሚያጋባ እይታ አስተዋላት…..የሆነ ነገር ይለኛል ብላ ብትጠብቅም ምንም አላላትም፡፡

"እዚህ ጉዳይ ውስጥ እጄ እንደሌለበት ጁኒየር የሚያምነኝ ይመስለኛል" ብላ አለቀሰች።

"በአንቺ ጉዳይ ስንጨቃጨቅ ስታይን ደስታ አሰከረሽ አይደል ?።››

በንዴት ጥርሶቿን አንቀረጨጨች"በኔ ምክንያት የምትጨቃጭቁበት ምንም ምክንያት የለም …ለማንኛውም.. ዛሬ ማታ በእርባታው ቦታ ላይ ለደረሰው ጉዳት እኔ ተጠያቂ ነኝ ብዬ አላስብም."

"ወደድሽም ጠላሽም ተጠያቂዋ አንቺ ነሽ። ጠላቶቻችንን አነሳስተሺብናል።"

ጭቅጭቃቸውን እልባት ሳያበጁለት መኪናዋ እሷ ቤት ጋር ደርሳ ቆመች….ገቢናውን ከፍታ ወረደች እና ከቤቷ ፊት ለፊት ቆመች። በሩ አሁንም ተገንጥሎ ገርበብ ብሎ እንደቆመ ነው።

ወደእሱ ዞረችና"ይህን በር የሚያስተካክል ሰው ልካለው ያልከኝ መስሎኝ ነበር።"አለችው

"እስከ ጥዋት ድረስ ታገሺኝ …ለዛሬው ከውስጥ ወንበር አስደግፈሽ መኝታ ክፍልሽን በራፍ ቆልፍሽ ተኚ..ደግሞም ሊነጋ ነው…ችግር የለውም››አለና መኪናውን አንቀሳቅሶ በቆመችበት ጥሏት ተፈተለከ፡፡አለም እቤቷ ከገባች በኃላ ራሱ መረጋጋት አልቻለችም…ገመዶ እንዳላት መኝታ ቤቷ ገብታ ከውስጥ በመቀርቀር አልጋዋ ላይ ኩርምት ብላ ስታሰላስልነው ነው ሊነጋጋ ሲል እንቅልፍ የጣላት …ጥዋት አንድ ሰእት ተኩል አካባቢ ሞባይሎ ጮኸ… ከአምስት ጥሪ በኃላ ከእንቅልፏ ባና አነሳችው፡፡
በሻከረ ድምፅ "ሄሎ?"

"ወ.ሪት አለም? አልቀሰቀስኩሽም አይደል? ከሆነ በጣም አዝናለሁ።››ልስልስ የሴት ድምጽ ነው፡፡አለም የደዋዬን ማንነት በድምጻ ለመለየት እየጣረች "አይ፣ ተነስቼ ነበር ››ስትል መለሰችላት፡፡

"ሳራ ጆ ነኝ"ድንጋጤ ሰውነቷን ሲወራት ታወቃት፡፡

በምንም አይነት ተአምር ሳራ የተባለች ቀዝቃዛ ሴት በዚህ ማለዳ ትደውልልኛለች ብላ ማሰብ አትችልም… ››

"ደህና ነሽ ወ.ሮ ሳራ?ችግር አለ እንዴ?"

ጁኒዬር የሆነ ነገር ሆነ ብላ ምትነግራት ነው የመሰላት፡፡በኋላ መልሳ ስታስበው በምን ስሌት ጂኒዬር የሆነ ነገር ቢሆን ለእሷ እንደማትነግራት ገባት፡፡

"አዎ ደህና ነኝ፣ ትላንትና ማታ ስለተናገርኩሽ የብልግና ንግግሮች ሳስብ በጣም ነው ያፈርኩት ።"

አለም የሴትዬዋን ኑዛዜ መስማቷ አስደንጋጭ ነው የሆነባት። እውነት ነው ብላም አምና ልትቀብል አልቻለችም፡፡"እረዳሻለሁ….በተፈጠረው አደጋ ተበሳጭተሽ ነበር።"ስትል መለሰችላት፡፡

"ቢሆንም ራሴን መቆጣጠር ነበረብኝ….እባክሽ ይቅርታ አድርጊልኝ››

‹‹አረ ችግር የለውም››ከዚህ ውጭ ምንም ልትላት ምትችለው ነገር እልነበራትም ፡፡
‹‹ዛሬ ከሰአት በኋላ ከእኔ ጋር ሻይ መጠጣት ብንችል ደስ ይለኛል…..እባክሽ?"

‹‹አለም ተኝቼ እያለምኩ ይሆን እንዴ?››ብላ ለማሰብ ተገደደች፡፡ ".. ችግር የለውም።"ነበር መልሷ፡፡

"ደህና ዘጠኝ ሰአት አካባቢ ይመችሻል?።"

"የት?"

"ለምን ፣ እዚህ እርባታ ግቢው ውስጥ ባለው ማረፊያ ቤታችት አናደርገውም…በዛውም የወደመውን ነገር መልሰው ለመገንባት እርብርብ ላይ ያሉ ሰራተኞችን እናበረታታቸዋለን…››

‹‹ችግር የለውም ..በቃ እገኛለው››

‹‹አመሰግናለው…..እስክንገናኝ ደህና ሁኚ።››

ስልኩ ተዘጋ፡፡አለም እንደደነዘዘች ነው፡፡የዚህች ሴትዬ ሁኔታ ምኑም አላማራት፡፡፡ስልኩ ላይ ለብዙ ሰከንዶች አፈጠጠች። ሳራ ለሻይ እንድትጋብዛት ያነሳሳት ምንድነው ? ሰዓቱ ደርሶ ከዚህ ግብዣ በስተጀርባ ያለውን ሚስጥር እስክታውቅ ድረስ ቸኮለች…ከዛ በፊት ግን መሄድ የሚገባት ቦታ አለ…..ገመዶ የላከው አናጺ መጥቶ በረፉን ከጠገነላት በኋላ ቀጥታ ወደጉዳዮ ሄደች፡፡

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
48👍8
አትሮኖስ pinned «#ቋጠሮ_ሲፈታ ፡ ፡ #ክፍል_ሀያ_አንድ ፡ ፡ #ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ /// ገመዶ እኩለ ለሊት ላይ ስልኩ ጮኸ…. "ምንድን ነው ነገሩ" በማለት እየተነጫነጨ በተኛበት እጁን ዘረጋና ስልኩን ከኮመዲኖ ላይ አንስቶ ጆሮው ላይ ለጠፈና ‹‹ሄሎ››አለ፡፡ ‹‹ኮማንደር መስማት አለብህ ብዬ ነው…ድንገተኛ ነገር ተከስቷል."ምክትሉ ነበር፡፡ ከመኝታው ተነሳና አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠ፡፡ "…ምንድነው የተፈጠረው?"…»
#ቀን

ሁሉንም ሞክረን ፥ ሁሉም ባይሳካ

የጨበጥነው ጥሪት ፥ ባይኖረው በረካ

ቆመን ስንጠብቀው ፥ ገፍቶን ላለፈን ቀን

ተስፋ ተሸልመን ፥ ናፍቆት ባያፀድቀን

ተቀበል ውዳሴ ፥ “ተመስገንን” እንካ

ሽሽግ አልበትን

የማልቀሻ አፀዱን ፥ በአቴን አትንካ።

🔘ኪሩቤል ዘርፉ🔘
👍128🥰2
#ጳጉሜን_ስወዳት

ተቀጥያ ሁና
ማምሻ ላይ ብትመጣም...
ልታከትም ዘመን፣
ቀናችን ጠውልጎ
አዲስ እያጓጓን ብታየንም ታመን
እሷስ ድልድይ ናት...!
ጭጋግና ፍካት ..
መሀል ያለች ቁጥር ፤
ተስፋን የምትጭር
ምን አቅም ባይኗራት
ፍዳን ልታሳጥር
እስቲ እንቁጠራት
ከአንድ ጀምረን
ጠንቅቀን አመሏን
እግዜር በቃ ካለን
3 የሚዘንበውን..
ሳንስት ጠበሏን።
🥰127
#ጳጉሜነት

ምን ባይደላህም
ቀን ቢያጥርህ አዳሜ፤
ራስህን መስለው
ልክ እንደ ጳጉሜ፤
አንሰህ ብትታይም
ግዝፍናህን ቁጠር ፤
አምስት ቀናትን ይዞ
ተስተካክሏልና ከወር!!!

🔘ሀብታሙ ወዳጅ🔘
👍15🔥21
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ሁለት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

////

ከኪሊንኩ ጀርባ ያለው የዶ/ር ኤሊያስ  ቢሮ ምናልባት አለም ከዚህ በፊት ካየቻቸው ቢሮዎች ሁሉ የተዝረከረከ ሆኖ ነው ያገኘችው፡፡

"ዶክተር ኤሊያስ እኔን ለማየት ስለተስማማህ አመሰግናለሁ።"

"ችግር የለም …ዛሬ ብዙም ስራ አልነበረኝም " ከቀጥታ ከጠረጴዛው አጠገብ ያለውን የእንጨት ወንበር ላይ ያሉትን መጽሔቶችን አስነሳና ጠረጴዛ ላይ በማድረግ ለአለም እንድትቀመጥበት አመቻቸላት፡፡

"አንቺን ሳይሽ ብዙም አልተገረምኩም

"አላት በቅንነት ።

"ለምን?"

"ዋና አቃቢ ህጉ ደውሎ አንዳንድ ጥያቄዎችን ልትጠይቂኝ እንደምትፈልጊ ነግሮኝ ነበር።"

"ዛሬ ከከተማ ውጭ ያለ መስሎኝ ነበር."

"አይ ከቀናት በፊት ነበር ሰሞኑን ትመጣለች ቡሎ የነገረኝ ።"

"ገባኝ…ለሊት የእሳት ቃጠሎ ቦታው እንስሳቶችን ለመርዳት ስትሯሯጥ ስለነበርክ…ዛሬ እንዲህ ንቁ ሆነህ ቢሮህ አገኝሀለው ብዬ አላሰብኩም ነበር።"

በመደነቅ‹‹እንዴ እዛ እንደነበርኩ በምን አወቅሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡

‹‹እኔም እንዳጋጣሚ እዛ ነበርኩ…አሁን ጊዜህን ሳልሻማብህ ቀጥታ ወደጉዳዬ ልግባ …የእናቴ የሰሎሜን ግድያን በተመለከተ መረጃዎችን እየሰበሰብኩ ነው….እባክህ አንተ በአቶ ፍሰሀ የእንስሳት እርባታ ድርጅት ውስጥ የእንስሳት ሀኪም ሆነህ እንደመስራትህ የምታውቀው ነገር ይኖር ይሆን ?" ስትል አሳዛኝ በሆነ የድምፅ ቅላፄ ጠየቀችው፡፡

"በእርግጥ እናትሽን አውቃታለው . እሷ በጣም አስደማሚ ሴት ነበረች. በእሷ ሞት ያላዘነ ሰው የለም ››

"አመሰግናለሁ፣ በዛን ወቅት በአቶ ፍሰሀ የእርባታ ድርጅት ውስጥ የእንስሳቱን ጤንነት ሚከታተሉት አባትህ እንደነበሩ ማወቅ ችያለው፡፡ "

" ልክ ነው …በዛን ወቅት አባቴ ነበር….እሱ ከሞተ በኋላ ግን ስራውን እኔ ተረክቤያለሁ." "አባትህ ስለ ሰሎሜ ግድያ ሁኔታ የሆነ ነገር ነግሮህ ይሆን?››

"በቀዶ ጥገና ቢላዋ መገደሏን በሰማ ጊዜ እንደ ሕፃን ነበር ተንሰቅስቆ ያለቀሰው››

"አባትህ እናቴ የተገደለለችበት መሳሪያ ከየት እንደመጣ አውቋል›?›

"አዎ …ያ አባቴ እንስሳቱን ለማከም የሚጠቀምበት መሳሪያ ነበር፣እናቴ ነበረች የሸለመችው የስሙ የመጀመሪያ ፊደል ተቀርፆበት ነበር ፡፡እንዴት አድርጎ ከቦርሳው እንደወደቀበት ነው ግራ የገባው፡፡››

"እንደዛ አይነት ግድ የለሽነት ከእሱ ባህሪ ጋር አይሄድም አይደል?"

"ትክክል ነሽ….አባዬ ለህክምና እቃዎቹ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያደርግ አይነት ሰው ነው
…በቆዳ በተለበጠ የእንጨት ሣጥን ውስጥ ነበር የሚያስቀምጣቸው…ያ ስለት ከሳጥኑ እንዴት እንደወደቀ ፈጽሞ ማወቅ አልቻለም ነበር, ››

"እናቴ በሞተችበት ቀን አንተ እዚያ ነበርክ?"

"ይህን ቀድመሽ ታውቂያለሽ ብዬ አስባለሁ። አባዬን ለመርዳት ትምህርት ከሌለኝ በስተቀር እዛ እገኝ ነበር …በዛም ቀን  አብሬው ሄጄ ነበር።››

"ገመዶ እዚያ ነበር?"

"በእርግጥ ኩማንደር እዚያም ነበረ።››

"ለሊቱን ሙሉ."

‹‹እሱን እርግጠኛ አይደለሁም…በመሀል አቋርጦ የሄደ ይመስለኛል››

"አባትህ የህክምና ቁሳቁስ የሚይዝበትን ሳጥን የሆነ ቦታ አስቀምጦ ዞር ብሎ ያውቃል?" ኤሊያስ ማሰላሰል ጀመረ … መልስ መስጠት እንደማይፈልግ ነገራት፡፡

‹‹ በዚያ ቀን በዛ አካባቢ ሌላ ማን ነበር?"ስትል ሌላ ጥያቄ ጠየቀችው፡፡

ለማስታወስ ሲጥር ተመለከተች‹‹‹ጁኒየር፣ ገመዶ፣ ጋሽ ፍሰሀ….እናትሽ….ስርጉት."

‹‹ ማን… ስርጉት ነበረች? ››

‹‹አዎ ነበረች …ከዛ ወደ ቤት መሄድ እንዳለባት ተናገረች እና አካባቢውን ለቃ ሄደች፡፡

‹‹ከግቢው ወጥታ ስትሄድ አይተሃታል….››

‹‹አይ መሄድ አለብኝ ብላ ስታወራ እንጂ ወጥታ ስትሄድ አላየኋትም….›› " ስለ ሊቁ ምን ማለት ይቻላል? እሱ በአካባቢው ነበር?"

‹‹እሱ ሁሌ  በሁሉም ቦታ የሚዞር..በሄድሽበት ቦታ የማታጪው አይነት ንክ ነበር ፣እውነቱን ንገረኝ ካልሺን ግን በዛን ቀን እሱን እዛ ቦታ እንዳየሁት አላስታውስም››

"እርሱን ካላየኸው በሰሎሜ ደም በተሸፈነ ልብሱ በቁጥጥ ስር ሲውል አልተገረምክም?"

‹‹በእርግጥ አልተገረምኩም…. ምን አልባት እኔ ሳላየው ጊቢ ውስጥ ሲዞዞር ከአባዬ ቦርሳ የወደቀውን ቢላዋ እንዳገኘው ገምታለው፣ ከዛ እናትሽን ገድሏታል ብዬ አስባለው.››

‹‹ነገር ግን ከዛ ሁሉ የአባትህ የህክምና መሳሪያዎች መካከል አንድ ቢላዋ ብቻ ሾልኮ መውደቁ ግራ መጋባት ውስጥ አይከትም… ?››

ዝም አላት…..፡፡

ይህ ዶ.ር የሶስቱም ተጠርጣሪዎች ጓደኛ ነው። በዛ ላይ በቋሚነት ለአቶ ፍሰሀ ተቀጥሮ የሚሰራ ሰው ነው፡፡የሚያውቀው ነገር እንኳን ቢኖር በምንም አይነት ተአምር አሳልፎ ሊሰጣቸው እንደማይፈቅድ አወቀች፡፡ከዚህ በላይ ጊዜዋን ማባከን ፋይዳ እንደሌለው ስላመነች ከመቀመጫዋ ተነሳችና አመስግናው ወደ ሁለተኛ ጉዳዮ አመራች፡፡
///
የእርባታ ድርጅት የእንቅስቃሴ አልባ ሆኗል ። የጽዳት ሠራተኞች ከቃጠሎ የተረፈውን ፍርስራሹን እና አመዱን እየሰበሰቡ እና እየጠረጉ በአካባቢው የቆመው መኪና ላይ እየጫኑ ነው። ኩማንደሩ በአካባቢው ወዲህ ወዲያ እየለ የሚሰራውን እየተመለከተ ነው፡፡ አለም ከመኪናዋ ስትወርድ አይቶታል፣ ነገር ግን እሷን ለማናገር ሲሞክር በአካባቢው የነበረው የእሳት አደጋ ተቆጣጣሪ ሰለጠራው ወደእዛ ለመሄድ ከተንቀሳቀሰ በኋላ ሀሳቡን ቀይሮ ቆሞ ጠበቃት፡፡ ደረሰችበት…ሰላም ይለኛል ብላ ስትጠብቅ

"እዚህ ምን እየሰራሽ ነው?"ብሎ ጠየቃት፡፡

‹ከሳራ ጋር ሻይ ልጠጣ ነው የመጣሁት።››

በመደነቅ አፍጥጦ ተመለከታ‹‹ከእሷ ጋር ደግሞ ከመቼ ወዲህ ነው ጓደኛ የሆናችሁት?››

“ሃሳብ የእኔ ሳይሆን የእሷ ነበር” አለችው።

"እሺ ተዝናኑ" አለና ፊቱን አዙሮ ሲጠራው ወደ ነበረው ሰውዬ ሄደ፡፡

እሷም ወደማረፊያ ቤቱ ተራመደች..አቶ ፍሰሀ  በቤቱ በረንዳ ላይ ቆሞ ነበር፣ ስትጠጋ ፍርሃቷ እንዳይታይ ለማድረግ ሞክራለች።

"እንዴት ነህ … ጋሽ ፍሰሀ?"

"  ሰዓት  አክባሪነትሽ  የሚደነቅ  ነው…እናትሽም  ልክ  እንደዚህ  ነበረች››አላት፡፡ለምን እንደመጣች እንደሚያውቅ ተረዳች

‹‹አመሰግናለው››አለችው፡፡

‹‹ምንም አይደል››

"ኩማንደሩ እሳቱን ያስነሳውን ሰው  በቁጥጥር ስር እንደሚያውለው  ተስፋ አደርጋለሁ። እኔም ተገቢን ፍትህ እንድታገኙ አስፈላጊውን ሁሉ አደርጋለሁ።"ስትል ቃሏን ሰጠችው፡፡

"አዎ፣ እኔም ተስፋ አደርጋለው… ሁሉንም ነገር ችላ ማለት እችላለሁ። ነገር ግን ያን የመሰለ ተወዳጁን የገመዶን ፈረስ እንዲሞት ያደረገውን ሰው ግን ይቅር አልለውም።ያን ፈረስ በማሳደግና በመንከባከቡ ይሰማው የነበረውን ኩራት እኔ ነበርኩ የማውቀው።"

በዚህ ጊዜ ጁኒዬር ከውስጥ ወጣ…በውብ ፈገግታ ተሞልቶ የሞቀ ሰላምታ ሰጣት፡፡ አለም"ወደ ውስጥ ብገባ ይሻለኛል… እናትህን ብዙ አላስጠብቃት" አለቸው ።
ጁኒየር እጁን ትከሻዋ ላይ ጫነና "እናቴ የትላንት ማታውን ጥፋቷን ማረም ትፈልጋለች። ግብዣዋን ስለተቀበልሽ በጣም ተደስታ ነበር። አንቺን ለማየት በጉጉት እየጠበቀችሽ ነው።››አላት

‹‹ጥሩ››ብላ ወደ ውስጥ ገባች፡፡
አገልጋይዋ በራፉ ድረስ መጥታ ተቀበለቻት።‹‹ግቢ።››ብላ ወደ ውስጠኛው ክፍል እየመራች ወሰደቻትና ከሳራ ጋር አገናኘቻት፡፡

ከሳራ ጋር ተጨባበጡና ጉንጭ ለጉንጭ ተሳሳሙ፡፡
አለም የክፍሉን ዙሪያ ገባ እየተመለከተች"እንዴት የሚያምር ክፍል ነው?!"

"ወደድሽው?።"

‹‹በጣም እንጂ…››
44👍7👏2
ሳራ  ክፍሉ  ውስጥ  ወደ  ነበረችው  ሰራተኛ  ዞረችና  "እባክሽ  በሩን  ዝጊው።
››አለቻት፡፡ሰራተኛዋ በሩን ዘጋችና ትታቸው ሄደች ፡፡ አለም እንድትቀመጥ ባሳየቻት ቦታ ተቀመጠች፡፡

"ስለጋበዝሽ አመሰግናለሁ። በጣም ጥሩ ሀሳብ ነበር።"

"ትናንት ማታ ስለተናገርኩሽ ነገር ይቅርታ መጠየቄ ግዴታ ነበር።"

" ግድ የለም.. አሁን እሱን እንርሳው።"

በሩ ተከፈተና ሰራተኛው ሻይ የያዘ ፔርሙዝና  ኩኪሶች ያየዘ አንድ ሰሀን አምጥታ በመሀከላቸው በሚገኝ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠችና እንደአመጣጧ ወጥታ ሔደች፡፡

ሳራ ፌርሙዙን አነሳችና ሻዩን የሁለቱም ብርጭቆ ላይ ከቀዳች በኋላ..‹‹ስኳር ስንት ማንኪያ ላድርግልሽ?"በማለት ጠየቀቻት፡፡

‹‹እባክሽ..ሁለት ይበቃኛል;;››አለም መለሰች፡፡

"አመሰግናለሁ።"

ሳንድዊች አንስታ እየጎረሰች ሻዬን ጠጣችና እና መልሳ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠች፡፡
ሳራ ቀጥታ ወደጉዳዮ ገባች

"ከፍሰሀ እና ጁኒየር በስተቀር የቀረኝ ቤተሰብ የለኝም።በልጅነቴ ከጀማይካ ወደእዚህ ይዘውኝ የመጡት እናትና አባቴ ነበሩ.. አሁን ሁለቱም ሞተዋል…በስመ ጀማይካዊ ካልሆነ በስተቀር እዚህ ኢትዬጵያ ውስጥ የቅርብ ዘመድ የለኝም፡፡››

‹‹ይሄን በመስማቴ አዝናለው…ያው እንደምታውቂው ዘመድን በተመለከተ እኔም ካንቺ ብዙ አልሻልም›› ስትል መለሰችላት፡፡

"ምን መሰለሽ …ሙታን በተቀበሩበት በሰላም እንዲያርፉ መፍቀድ የተሻለ እንደሆነ እየነገርኩሽ ነው፡፡››
አለም የሳራ የንግግሯ አቅጣጫ እየገባት ነው ፡፡

"ስለእናቴን ነው የምትናገሪው?"

"በትክክል ….ይህ የአንቺ ምርመራ መላ ቤተሰቤን ሰላም እየነሳ ነው›፡፡››

"ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ እጠይቃለሁ፣ ነገር ግን  በእኔ እቅድ ላይ ምንም የሚደረግ ለውጥ የለም።"ስትል መለሰችላት፡፡

"ወንበዴዎች ንብረቴን አወደሙት፣ ዛሬ የእንስሳቱን ህይወት አደጋ ላይ ከጣሉ ነገ ደግሞ ባሌን ወይም ልጄን ለማጥቃት ከማድባት ወደኃላ አይሉም፡፡ ››

አለም "ይህ አሳዛኝ ክስተት ነበር ። በዚህ ጉዳይ ምን ያህል እንዳዘንኩ ልነግርሽ አልችልም" በማለት ሴትየዋን እንድትረዳ ተማፀነች፡፡

ሳራ ጆ በረጅሙ ተነፈሰች። "እናትሽ ከጁኒየር እና ገመዶ ጋር ስለነበራት ግንኙነት ምን ያህል ታውቂያለሽ?"

"አያቴ የነገረችኝን ብቻ፣ እዚህ ሻሸመኔ ከመጣው በኃላ ካነጋገርኳቸው  የተለየያዩ ሰዎች የሰበሰብኩት  የተወሰነ መረጃም አለ።"

"እንደ መንትያ ወፎች አይነት ነበሩ… ለራሳቸው ትንሽ ቡድን ፈጥረው ነበር. ጁኒየር ከእነሱ ጋር እንዲገናኝ አልፈልግም ነበር….ገመዶ በሁሉም ነገር የሰከረ የከተማ ልጅ ነበር። እና እናትሽም እንደዛው ...ከእነሱ ጋር እንዲጣመር የማልፈልግበት ብዙ ምክንያቶች ነበሩ።"

"አንድን ጥቀሺልኝ."

"በዋነኛነት በእሷ እና በገመዶ መካከል ስላለው ሁኔታ ጁኒየር ሁል ጊዜ ሁለተኛ ምርጫዋ እንደሆነ አውቅ ነበር። የተሻለው የቱ እንደሆነ እንኳን መለየት የማትችል ከንቱ ነበረች፡፡ ስለዚህ ጉዳይ ለጁኒየር ላስረዳውና ላስጠነቅቀው ብሞክርም ስለሚወዳት ሊሰማኝ አልፈቀደም። እንደፈራሁት  አፍቅሯት ነበር።" በድንገት ዓይኖቿ በአለም ላይ አተኩሩ።የሳራ አይኖች በክፋት ጠበቡ።

"እናትሽ ተንኮለኛ ነበረች።››

"እስከዚህ ነጥብ ድረስ አለም ምላሷን በጥንቃቄ ተቆጣጥራ ነበር። ነገር ግን ጋባዦ በሟች እናቷ ላይ ምትሰነዝረውን ልቅ ንግግር መታገስ አልቻለችም፡፡

"ከዚያ የስም ማጥፋት የተለየ አስተያየት አለኝ ወይዘሮ ሳራ።››

ሳራ ግድ የለሽ በሆነ ሁኔታ እጆን አወናጨፈችን " ግድ አይሰጠኝም…የተናገርኩት እውነቴን ነው፤እሷን ባገኘኋት ጊዜ ቆንጆ ነበረች፣ በጋለ ስሜት ነበር የምታወራው። የሚወደድ አይኖች ነበሯት ። ጮክ ብላ ነበር የምትስቀው፣ ተጫወች ነበረች፣ ስትጠጣ በጣም ስሜታዊ ስለምትሆን እራሷን መቆጣጠር አትችልም ነበር፡፡ በጣም ሐቀኛ ትመስላለች ግን አልነበረችም፡- ስትናገር በኩራት ነው፡ ‹‹ሰዎች የሚሰማቸውን በግልጽ ቢናገሩ ዓለም የተሻለ ሊሆን ይችል ነበር›› ብላ የምትጎርር አይነት ሴት ነች።ወንዶች ሁሉ ያለ ልዩነት ይፈልጓት ነበር፡፡ ያገኘችውን ወንዷች ሁሉ በፍቅር እንዲወድቁላት በማድረግ እርካታ የሚሰማት አይነት አደገኛ ሴት ነበረች፡፡ ››

"እራሷን ለመከላከል የማትችልን  ሴት ከዚህ በላይ  እንድታጣጥያት  አልፈቅድልሽም. ንግግርሽ ከስርዓት ያፈነገጠ ነው ወ.ሮ ሳራ፡፡››

ስትገባ እንደ ግሪንሃውስ ንፁህ አየር የሞላው የነበረ ክፍል አሁን የታፈነ ይመስላል። ለቃ መውጣት ፈለገች፡፡

"መሄዴ ነው"አለቻት፡፡

"ገና አልጨረስንም.እናትሽ ከራሷ በላይ ኩማንደሩን ትወደው ነበር።"

"ታዲያ ይሄ ጉዳይ አንቺን  እንዴት ሊያሳስብሽ ቻለ?"

"ምክንያቱም ጁኒየርን በዚህ ጉዳይ ውስጥ ስላስገባችው ነው የሚያሳስበኝ ..አያትሽ ያቺ ደደብ ሴት በልጆቻችን መካከል መግባቷን ስላወቀች በጣም ተናደደች:: ጁኒየር ሰሎሜን እንዲያገባ የፈቀድኩኝ አስመስላ መንቀሳቀስ ጀመረች" ስትል ተሳለቀች::

‹‹አልገባኝም››

"አያትሽ አንድ ጊዜ ደውላልኝ የወደፊት አማቶች እንደመሆናችን መጠን በደንብ እንድንተዋወቅ ሀሳብ አቀረበችልኝ፣ በእግዚአብሔር ስም.. በዛኑ ጊዜ መሞት ነበር የፈለኩት
›› አለችና .. በንቀት ሳቀች።

‹‹ከዛ ምን አልሻት?››አለም በንዴት እየተንተከተከች ጠየቀች፡፡

"አለም ምራቴ የምትሆንበት ምንም አይነት እድል አልነበረም። ይህንንም ለአያትሽ በግልፅ ነበር የነገርኳት።እና ምን ለማለት ፈልጌ መሰለሽ …ከቅርብ ጊዜ ወደዚህ እሱ ስለ አንቺ ብቻ ነው የሚያስበው፤ ልክ ከእናትሽ ጋር እንደነበረው."

"ወ.ሮ ሳራ አትስጊ…በመካከላችን የፍቅር መጠላለፍ በፍፁም ሊኖር አይችልም። ምናልባት ይህ ምርመራ ከተፈታ በኋላ ጓደኛሞች ልንሆን እንችል ይሆናል።››

ሳራ "እናትሽም እንደዚሁ ነበር የምትለው…በኋላ ግን ጓደኝነታቸውን አላግባብ ተጠቀመችበት ፡፡ምክንያቱም ጓደኝነታቸው ወደጋብቻ ያድጋል የሚል ስውር ተስፋ ነበራት፡፡

አንቺም እንደ እናትሽ ምርመራውን እንደሰበብ አድርገሽ ከእሱ ለመቀራረብ እና ልቡን ለመስረቅ እየተጠቀምሺበት ነው።››አለቻት

"ይህ በበፍጹም እውነት አይደለም."

"እውነት ካልሆነ ለምን ወደዚህ መምጣት አስፈለገሽ?"ሳራ በመንገሽገሽ ጠየቀች፡፡
"የመጣሁበት አላማማ ግልፅ ነው…እናቴ ለምን እንደተገደለች እና ማን እንደገደላት ለማወቅ እፈልጋለሁ."

ጣቷን በቀጥታ ወደ አለም ልብ እየጠቆመች"እናትሽ የተገደለችበት ምክንያቱማ አንቺ ነሽ!" አለቻት ። አለም ይህንን ንግግር ከዚህ በፊት ከገዛ አያቷም አንደበት ሰምታ ነበር …አሁን ከወ.ሮ ሳራ ለሁለተኛ ጊዜ ስትሰማው የመሬት መንቀጥቀ የተነሳ ያህል ነው መላ አካሏን የነዘራት፡፡

‹‹ምን ማለት ነው?››

"አንቺ የሰሎሜ ዲቃላ ልጅ ነሽ ››
አለም ስለታም ብረት በሆዷ ውስጥ እንደተሻጠ አይነት ህመም ተሰማት፡፡

‹‹አልገባኝም›› "

የምናገረው ግልፅ እኮ ነው…ከጋብቻ ውጭ የተወለድሽ ህገ ወጥ ልጅ ነበርሽ"

"ይህ ውሸት ነው" አለም ትንፋሿን ካደት። "እናቴ ከጎበና ጋር ተጋብታ ነበር። የሰማንያ ወረቀታቸው አይቻለው ።"ከተቀመጠችበት ተነስታ ቆመች፡፡
41👍1
"አይደለም…..ክርምት ቤተሰቦቼን ልጠይቅ ብላ ኮፈሌ ሄዳ ነበር….ግን ስትንዘላዘል አንቺን ፀንሳ ተመለሰች….አላወቀችም ነበረና ሀገር ሳላም ነው ብላ ከገመዶም ሆነ ከልጄ ጋር ያላትን ግንኙነት ቀጥላበት ነበር….በኃላ ግን ማርገዟን አወቀች….ማስወረድም አልቻለችም መሰለኝ መልሳ ወደኮፈሌ ተመልሳ ጠፋች….ዘመዶቾ ልጁን አስገድደው እንዲያገባት አደረጉ
…ግን ሰማንያውን ፈረመ እንጂ አንድ ቤት እንኳን አልገቡም ነበር…ከዛሬ ነገ እቤት ተከራይቶ እና እቃ አሞልቷ ይጠቀልለኛል ብላ ስትጠብቅ እሱ ሹልክ ብሎ ውትድርና ተቀጠረና ሄደ… እሷም የተቀበተተ ሆዷን እና የሰማንያ ወረቀቷን ይዛ አይኗን በጨው አጥባ ወደእዚህ ተመለሰች….ደጋግሜ እንደነገርኩሽ ሁሉንም ወንዶች የሚያደነዝዝ አዚም ስላለባት ሁለቱም ቢበሳጩባትም ከህይወታቸው ሊያስወግዷት አልፈቀዱም…..እስከነ ዲቃላዋ ይንከባከቦት ጀመረ…. ከዛ አንቺም ተወለድሽ.. ዲቃላ ያስታቀፋትም እዛው ወታደር ቤት እንደገባ መሞቱን መርዶ መጣላት፡

"ውሸትሽን ነው!" አለም እንዳትወድቅ ስለፈራች  የወንበሩን እጄታ ያዘች።

"ለምን እዋሻኛለሁ?ቤተሰቦቼን ከአንቺ የበቀል ጥፋት ለመጠበቅ እየሞከርኩ ነው። ፍሰሀ በአመታት ልፋት የገነባውን ሁሉ እንድታጠፊ አልፈቅድም። በቤተሰቤ ውስጥ አለመግባባት እንድትፈጥሪ አልፈቅድም። ከዚህ በፊት እናትሽ እንደዛ አድርጋ ነበር… አሁን.. ግን አልፈቅድም።

"ሴቶች… ሴቶች." ጁኒየር እየሳቀ ወደ ክፍሉ ገባ።‹‹ ይህ ጩኸት ምንድነው? ሸረሪት ተመለከታችሁ እንዴ?"

በመካከላቸው ያለውን ጥላቻ ሲታዘብ ቀልዱን አቆመና ግራ በመጋባት እያፈራረቀ ያያቸው ጀመር ። በአቅራቢያው መብረቅ የወረደ ይመስል አለም ደርቃና ገርጥታ ተመለከታ፡፡

"እናቴ? አሌክስ? ምን ተፈጠረ?"

አለም ምንም ሳትናገር ወንበሩ ላይ የተንጠለጠለውን ቦርሳዋን አነሳችና ከክፍሉ በፍጥነት ወጣች እና ሄደች ፡፡ጁኒየር አለምን ከኋላ ተከትሎ ከመግቢያው በር ጋር ደረሰባት ፡፡

"ምንድን ነው የተፈጠረው?"

አለም እንባዋን እንዳያይ ፊቷን በእጆቾ ሸፈነች።

"ምንም።"

" ሻይ ለመጠጣት እንደተቀጣጠራችሁ ስሰማ እኮ በጣም ደስ ብሎኝ ነበር››

"ሻይ? ሃ!ሻይ እንድንጠጣ አይደለም የጋበዘችኝ››

‹‹እና ለምንድነው?››

እንባዋ እንዳይወርድ ለማድረግ ብላ ዓይኖቿን ብታሽም አልተሳካላትም "ለነገሩ ስለነገረችኝ ማመስገን አለብኝ ።"

"ምንድነው የነገረችሽ?" "እኔ ዲቃላ መሆኔን ."

የጁኒየር ፊት በድንጋጤ ባዶ ሆነ።

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍4418😢1
🌼ውድ የቻናሉ ተከታዎችእንኳን ለ 2018 ዓ.ም አዲስ ዓመት በሠላም  በጤና አደረሳችሁ

❤️በዓሉ የሠላም፣ የጤና፣ የደስታ እና የፍቅር አመት እንዲሆን  ለሁላችሁም ረጅም እድሜን ከጤና ጋር እንመኛለን !

   🌼መልካም አዲስ ዓመት ለሁላችን🌼
@atronosee
         
5🥰2
አትሮኖስ pinned «#ቋጠሮ_ሲፈታ ፡ ፡ #ክፍል_ሀያ_ሁለት ፡ ፡ #ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ //// ከኪሊንኩ ጀርባ ያለው የዶ/ር ኤሊያስ  ቢሮ ምናልባት አለም ከዚህ በፊት ካየቻቸው ቢሮዎች ሁሉ የተዝረከረከ ሆኖ ነው ያገኘችው፡፡ "ዶክተር ኤሊያስ እኔን ለማየት ስለተስማማህ አመሰግናለሁ።" "ችግር የለም …ዛሬ ብዙም ስራ አልነበረኝም " ከቀጥታ ከጠረጴዛው አጠገብ ያለውን የእንጨት ወንበር ላይ ያሉትን መጽሔቶችን አስነሳና…»
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ሶስት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///

"ምንድነው የነገረችሽ?"

"እኔ ዲቃላ መሆኔን ."

የጁኒየር ፊት በድንጋጤ ባዶ ሆነ።

"እውነት ነው አይደል?"
ጁኒየር እጆቹን ዘረጋና እቅፉ ውስጥ አስገባት… እንባዋ በመጨረሻ የዐይን ሽፋኖቿን ሞልተው ያለከልካይ ፈሰሰ።

"ሰሎሜ ከኮፈሌ ተመልሳ መጣች። ከገመዶ ጋር ለመታረቅ ተዘጋጅታ ነበር።ፍቅራቸውን ለማደስ ተስማምተው ነበር …የመጋባት እድል ሁሉ ነበራቸው…በመሀል ግን ለማንኛችንም ሳትነግረን መልሳ ጠፋች….በኋላ ነው አንቺን ማረገዟን ስላወቀች እንደጠፋች ያወቅነው፡፡››ሲል አስረዳት፡፡

በእፍረት ፊቷን በእጆቿ ሸፈነች።
" ኦ አምላኬ በጣም ቢጠላኝ አይገርምም።››

ጁኒየር እጆቿን ከፊቷ ላይ አንስቶ በቅን ልቦና የሚወዳቸውን ጥቆቁር አይኖችን እየተመለከተ።

"ገመዶ አንቺን አይጠላሽም አሌክስ። ማናችንም ብንሆን አንጠላሽም…ያ ከአመታት በፊት ተጋፍጠን በይቅርታ ያለፍነው ጉዳይ ነው››

በንግግሩ በምሬት ሳቀች።‹‹ለምን አያቴ ሁሌ እኔ ላይ ጥብቅ እንደምትሆን እያሰብኩ እበሳጭ ነበር …በስንት ሰዓት ከቤት እንደወጣው? በስንት ሰዓት እንደተመለስኩ..?ከማን ጋር እንደነበርኩ ከአግባቡ ያለፈ ቁጥጥር ታደርግብኝ ነበር…ምክንያቷ አሁን ነው የገባኝ
…ለካ እናቴን ያጋጠማት ነገር እንዳያጋጥመኝ ፈርታ ነው፡፡አሁን ነው የገባኝ፡››

"ይሄ ከሃያ አምስት አመታት በፊት የሆነ ድርጊት ነው ፣ አሌክስ አሁን ስለዛ ማሰብ አቁሚ "

"አያቴ በእውነት እኔን ለምን እንደማትወደኝ የሚያብራራልኝ ታሪክ ነው… የሰሎሜን ህይወት አበላሽቻዋለሁ…እና ለዛ ፈጽሞ ይቅር ሳትለኝ ነው የሞተችው…. ሰሎሜ ገመዶን አጥታለች …ፍቅራቸው እንዳይሆን ሆኖ ተሰባብሯል … እና ሁሉም የሆነው በእኔ ምክንያት ነው››.

‹‹ኦህ፣በእግዚአብሔር !ተረጋጊ እንጂ!"
አለም ከእቅፉ ወጣችና ወደ መኪናዋ ሮጠች…መኪና ውስጥ በመግባት አስነሳችና አካባቢውን ለቀቀች።

."ምንድነው ነገሩ?" አለም ወደ መኪናዋ አቅጣጫ ስትሮጥ ያያት አቶ ፍሰሀ ጠየቀው።

"ሁለታችሁም እሷን ተዋት" ሳራ ከውስጥ እየወጣች ለባሏ መለሰች፡፡

ጁኒየር ወደ እናቱ ዞረና።

"እማዬ እንዴት እንዲህ ታደርጊያለሽ? እንዴት ልጅቷን እንዲህ ትጎጂያታለሽ?"

"ልጎዳት አስቤ አይደለም የነገርኳት፡፡››

"ምን ነግራት ነው?" አቶ ፍሰሀ ጠየቀ ፡፡

ጁኒየር “በእርግጥ ጎድተሻታል። ደግሞ አቅደሽበት ነው ያደረግሽው… ለምን ነገርሻት?"

‹‹ምክንያቱም እሷ ማወቅ ስላለባት። አለምን የምትጎዳት እራሱ አለም ብቻ ነች። ሸቅዠቷን እያሳደደች ነው። የምትፈልጋት አይነት ቅድስት የሆነች እናት በሰሎሜ ውስጥ አልነበረችም። ሰሎሜ ምትባል ድንቅ እናት እንደነበረቻት በማይረባ ጭንቅላቷ ደምድማለች። እናቷ ምን ያህል ተንኮለኛ እና ሀጥያተኛ እንደሆነች ልጅቷ ማወቅ አለባት.. እናቷ ስትማግጥ እሷን ዲቃላ እንዳረገዘቻት የማወቅ መብት አላት››

" አንቺ እኮ ጤነኛ አይደለሽም!" አቶ ፍሰሀ ተበሳጨባት፡፡

አቶ ፍሰሀ በጸጥታ ወደ መኝታ ቤት ገባና ከኋላው በሩን ዘጋው፡፡ሳራ በአልጋዋ ላይ ያሉትን ትራስ ደራርባ ተደግፋ መፅሃፏን እያነበበች ነበር…እሱን ስታይ መፅሀፉን ከደነችና አጠገቧ ያለው ኮመዲኖ ላይ አስቀመጠች ።

ወደአልጋው ቀረበና " ላናግርሸ እፈልጋለሁ።"አላት፡፡

"ስለ ምን?"

‹‹ዛሬ ከሰአት በኋላ ስለተፈጠረው ነገር።››
"ራስ ምታት እየፈለጠኝ ነው…ለእራት ወደታች ያልመጣሁትም ለዛ ነው"

‹‹የሆነ መድሀኒት አልወሰድሺበትም?"

"አዎ ወስጄለሁ…አሁን በመጠኑ እየተሻለኝ ነው ።"የሳራ የራስ ምታት በትዳራቸው ልክ አብሯት የቆየ ህመም ስለሆነ የተለመደ ነው፡፡

በአልጋው ጫፍ ላይ ተቀመጠ እና አቀርቅሮ ሀሳብ ውስጥ ገባ፡፡

" ምንድነው ፍሰሀ ?አሁንም የሚያሰጋን ችግር አለ እንዴ?››ጠየቀች፡፡

"አይ..ሁሉም ነገር ሰላም ነው።"

"ታዲያ ለምን ታስባለህ…?እግዚአብሔር ይመስገን ብቸኛው የሞተው ፈረስ የገመዶ ነው
።››
አቶ ፍሰሀ ምንም አስተያየት መስጠት አልፈለገም ። ሳራ ጆ ለገመዶ ያላት ስሜት ፈጽሞ አይለወጥም፤በዚህ ጉዳይ ከእሷ ጋር መነጋገር ጥቅም አልባ እንደሆነ እርግጠኛ ነው፡፡ከእሷ ጋር ሊወያይ የመጣው ስስ ስለሆነ ጉዳይ ነው። ቃላቱን በጥንቃቄ ለመምረጥ ትንሽ ጊዜ ወሰደበት.

"ሳራ ዛሬ ከሰአት በኋላ -……" "በጣም ተበሳጭቼ ነበር" አለችው፣ ፡፡

" ተበሳጭተሽ ነበር?" ፍሰሀ ትዕግሥተኛ ሆኖ ጠየቃት፡፡ወደ ድምዳሜው ከመዝለሉ በፊት ከእሷ ወገን ያለውን የታሪኩን ገጽታ መስማት ፍልጓል።

"የአለምን ስሜትስ የጎዳሽ አይመስልሽም…?"

"ዲቃላ መሆኗን ስላወቀች ብቻ አይደለም የተናደደችው….እሷ በተፈጥሮዋም ብስጩ ነች:: "

"እኔ በእሷ ቦታ ብሆን አይገርመኝም… ወላጆቼ የጋብቻ ሰርተፊኬት እንዳላቸው በጭራሽ አጣርቼ አላውቅም.., እና ባይኖራቸውም ምንም አይመስለኝም ነበር.››

" ሁሉም ሰው ለነገሮች ያለው ምላሽ የተለያየ ነው››

‹‹ አለም ግን ስሜታዊነት የሚያጠቃት ወጣት ሴት ነች።"

"እሷ ይሄን ታሪክ ለመቀበል የሚያስችል ጥንካሬ እንዳላት አምናለው."ስትል መለሰችለት

"በእርግጥ የምትይውን ያህል ጥንካሬ እንዳላት እርግጠኛ አይደለሁም።በረንዳ ላይ ቆሜ እያየችኝ እኔን እንኳን ሀሳትሰናበተኝ ነው ገፍትራኝ ሮጣ የሄደችው፡፡››

የሳራ ፈገግታ ተሰበረ። "ስለነገርኳት ትወቅሰኛለህ? ስህተት የሰራው  ይመስልሃል?"ስትል ጠየቀችው፡፡

በዛ ልብን በሚሰረስር የግሏ የሆነ ልዩ እይታ ስታየው፣ ልቡ ቀለጠ። ሁል ጊዜም የዚህ አይነት አስተያየት ስታየው የሚሆነው እንደዚሁ ነው። ፍሰሀ በስሱ ይዳብሳት ጀመር፡፡

‹‹ውዴ ስለነገርሻት አልወቅስሽም። ግን የነገርሽበት መንገድ እንደዚህ ባይሆን ጥሩ ነበር፡፡ እንደዛ ከማድረግሽ በፊት ከጁኒዬር እና ከእኔ ጋር መመካከር ነበረብሽ…በህይወቷ ሙሉ ባታውቀው የሚሻል ታሪክ ነበር፡፡››

"አልስማማም" ስትል ሳራ ተከራከረች።
አቶ ፍሰሀም "እናቷ እና አባቷ አብረው ከተኙ በኃላ አለመጋባታቸው ወይ መጋባታቸው በእሷ ልጅነት ላይ አሁን ምን ለውጥ ያመጣል? ይህ በቡዙ ወጣት ሴቶች ህይወት ላይ የሚያጋጥም በጣም የተለመደ ነገር ነው..››አላት፡፡

"ልጅቷ ስለ ሰሎሜ ያላት አመለካከት ላይ ግን ለውጥ ያመጣል። ››

‹‹እንዴት?››

‹‹ሰሎሜ ልጅቷ የምታስባትን አይነት ቅድስት ሴት አይደለችም…ይሄን ማወቋ የእሷን የግድያ ጉዳይ ለማወቅ የምታደርገውን ልፋትና ጥረት ቆም ብላ እንድታይ ያግዛት ይሆናል….ይልቅ ከአሁን በኃላ ሁላችሁም ከአለም ጋር መገናኘቱን እና መወያየቱን ማቆም አለባችሁ፡፡››

"ለምን?"ግራ ገብቶት ጠየቀው፡፡

"ለምን? ምክንያቱም እሷ እኛን ለማጥፋት እየሞከረች ነው…ለዚህ ነው. እሷን ለመፋለም የወሰንኩ…. ያለኝን ጥይት ነው የተጠቀምኩት….አንተን እና ጁኒየርን ለመጠበቅ እየሞከርኩ ነበር."

በእውነቱ፣ ፍሰሀ እንደ አለም ያለ በራስ መተማመን የነበራትን ሴትን ለመጋፈጥ ለሣራ ትልቅ ድፍረት እንደሆነ አሰበ። ያደረገችው ስህተት ቢሆንም ሳራ ያደረገችውን ነገር ያደረገችው ቤተሰቧን ልትጠብቅ እንደሆነ ተረድቷታል። የጀግንነት ጥረቷ ከትችት የተሻለ ነገር ይገባዋል ብሎ አሰበ እና ጎንበስ ብሎ ግንባሯን ሳመ።

ለስለስ ባለ ንግግር" የትግል መንፈስሽን አደንቃለሁ… ግን ማናችንም ያንቺን ጥበቃ አንፈልግም ።"አላት፡፡
47👍3
በሃሳቡ ሳቀች። "እንዴት እንደ አንቺ ያለች ደካማ ሴት ከመካከላችን ትልቅ እና የታጠቁ ወንዶችን ልትጠብቅ ትችላለች ለማለት ነው?አታስተውልም እንዴ ጁኒየር እኮ ከእሷ ጋር ፍቅር እየያዘው ነው."

"ታዲያ ቢይዘው ምን ችግር አለው ?" አለ በሚያብረቀርቅ ፈገግታ። ሳራ "እናቷ ልቡን ሰብራው ነበር ፣ ያ አያስጨንቅህም?"።
ፍሰሀ ፊቱን አኮሰታትሮ፣

"ያ ከረጅም ጊዜ በፊት የሆነ ነው። እና አለም እንደ እናቷ አይደለችም።"

"በዛ እርግጠኛ መሆን አልችልም." አለችና ሳራ ወደ ኮርኒሱ ተመለከተች።

"አለም እንደ ሰሎሜ ተለዋዋጭ እና ?ገራሚ ሴት አይደለችም….እንደውም እሷ በጣም ጎበዝ ሴት ነች ፣ ምናልባት ለጁኒየር የምታስፈልገው እንደእሷ አይነት ሴት ልትሆን ትችላለች
… እስከአሁን ብዙ ሴቶች ለማግባት ሞክሮ አንዱም ትዳር ሊሰምርለት አልቻለም፤እንደ እሷ  ምን እንደሆነ የምትነግረው ሴት ይፈልጋል ።"

"በነገራችን ላይ አሁን የት ነው ያለው? አሁንም እንደተናደደብኝ ነው?" ብላ በጭንቀት ጠየቀች።

" ተበሳጨቷል … ነገር ግን እንደ ሁልጊዜውም በመስከር ብስጭቱን ሊረሳ ሄዷል ." ሁለቱም ተሳሳቁ።

" ተጠንቅቆ እንደሚነዳ ተስፋ አደርጋለሁ።"
‹‹ምን አልባት …ሌሊቱን እዛው የሚያሳልፍ ይመስለኛል ." "ወይ ተው እንጂ ?"
"እንደዛ ቢያደርግ …አይገርመኝም" አለ ፍሰሀ

"አለም እራሷን ለማስተካከል የተወሰነ ጊዜ ያስፈልጋታል። ዛሬ ማታ የሚፈልገውን መጽናኛ የምትሰጠውን ሌላ ሴት ያገኛል።››
የአቶ ፍሰሀ አይን  ወደ ሚስቱ ዳሌ  ዝቅ አለ፣ …እጁ ሰውነቷን ሲዳብሳት  በድካም ቃተተች።

"እናንተ ወንዶች ! ስለእዛ ጉዳይ ብቻ ነው የምታስቡት? -"ተነጫነጨች "እንዲህ አይነት ቋንቋ አትጠቀሚ። ጭካኔ ነው።››
‹‹ ዛሬ ማታ ይህን ማድረግ አልፈልግም። ራስ ምታቴ እየተመለሰ ነው።››
የእሱ መሳም ተጨማሪ ተቃውሞዎችን አስነሳ. ። እሷ ሁል ጊዜ መቃወሟ የማይቀር ነው፡፡ ግን በጭራሽ አይቀበላትም። ከስሜታዊነት ይልቅ በግዴታ ስሜት ለእሱ ምላሽ መስጠቱ እሷን ከመፈለግ አግዶት አያውቅም። እንደውም በተቃራኒው ፍላጎቱን ከፍ ያደርግለት ይሆናል ። ፈጥኖ ልብሱን አውልቆ አንሶላውን ገልጦ ገባ ፡፡

ሳራ የሌሊት ልብሷን ጫፍ ወደላይ ሲሰበስባ እጁን ያዘችና ከለከለችው፡፡ አቶ ፍሰሀ ወደእሷ ተጠጋና ጉንጯን ሳመ እና አቀፋት። ለስላሳ እና፣ ጥሩ መዓዛ ያለው ቆዳዋን መዳበስ ክፉኛ ፈልጎ ነበር … ከእሷ ግር ፍቅር መስራት አምሮታል፡፡

"ፍሰሀ አሁን ተኛ … ይህን የጀመርኩትን ምዕራፍ መጨረስ እፈልጋለሁ" አለችው።

እንደ ፍቅሯ ደረቅ እና ህይወት የሌለውን ልቦለድዋን እንደገና ከፍታለች። ፍሰሀ ከማንበቢያዋ መብራት ርቆ ወደ ሌላኛው የአልጋው ጠርዝ ተጠጋና ፊቱን አዞሮ ተኛ ፡፡ እንደፍላጎቱ ስላልሆነችለት ተበሳጭቶ ነበር፡፡

ይቀጥላል

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍3217
አንቺ ?
አንቺ እንቁጣጣሽ
ምናባሽ ልትሰሪ መጣሽ?


አሁንም ግፍ አይበቃሽም
ዘንድሮም ለምለም ትያለሽ
ካቀፍሽው ቅጠል ባለፈ
የለመለመ ምን አለሽ?

ካቻምናም አምናም መተሻል
አቅፈንሽ አጥነን ደግሰን
አመትሽ ውበቱ ላይቆይ
እያደር ሊያተራምሰን

አንቺ ?
አንቺ እንቁጣጣሽ
ምናባሽ ልትሰሪ መጣሽ?

አምና ተስፋ አስደረግሺኝ
ደክሜ ቤቴን ሰራሁኝ
አልቅሼ ልገባበት ስል
ይፈርሳል ሁሉ ሰማሁኝ
አሁንም ተስፋ አልቆረጥኩም
ቃልሽን ስመላልሰው
አመትህ ተባርኳል ብለሽ
የላክሺኝ እንደ ሞኝ ሰው
ስታገል ከማይሽር ህይወት
መቀመቅ ነፍሴን ሲውጣት
ወደፊት ፈቀቅ እያልኩኝ
ሞት ልቤን እንዳይለውጣት

"አበባ አየሆሽ" አትበዪኝ
አበባ አልቸገረኝም
ዘፈንሽ አንገሽግሾኛል
ጨዋታሽ አይሰማኝም
በያመት ደምቀሽ ስትመጪ
ህፃን ልጅ ለምትመስዪው
ግጥሙን በምነግርሽ ቃል
ስትዘፍኚ አስተካክዪው

"የሀገሬ ልጆች ውጡ በተራ
ቅስም ሰብሬ  ሰው እስክሰራ
እንኳን ሰውና  የለኝም እድል
ሁሌ መጣለው አመት ላጎድል
አመት አጉድዬ ስገባ ቤቴ
ደስታ ይሰማታል የእንጀራ እናቴ"
አደዪ
የሞት ጉዳዪ
"ኡኡ" በዪ

እንደዚህ ብለሽ ዝፈኚ
ግጥሙን አስተካክለሽው
በቃ አንቺም እንዳገሬ ሰው
ጊዜን ነው የተማመንሽው?

"ሆ ብለሽ መጣሽ
ሆ ብለሽ
ሆ ብለሽ መጣሽ
ሆ ብለሽ"

ሆሆሆሆ!

አታፍሪም ደግሞ
ልክ እንደ ንፁህ እንዳልበደለ
ተስፋሽ ምስኪኑን እየገደለ
ከዘመን ዘመን ማትለወጪ
ጉድ ያዘለ አመት አቅፈሽ ምትሰጪ
ሆ ብለሽ መጣሽ?
ሆ ብለሽ ውጪ!

ለተድላ ሳይሆን
ለሞት ዋዜማ ፡ እያስጨፈርሺኝ
በመጣሽ ቁጥር
ሆ የምልልሽ ፡ ሞኝ አደረግሺኝ?

አሁን ንገሪኝ
ስለ አመትሽ
ይብስብኛል ወይስ ድናለው?
ዘፈኑን ተዪ ፡ ያንቺን ስሞታ ለምጄዋለው

ባለእንጀሮችሽ በተራ ገቡ
አዝማች አባትሽ ሌላ አገቡ
እንጨቱን ሰብረሽ ቤት እስክትሰሪ
ለእንጀራ እናትሽ ሳትናገሪ
እድጅ አድረሻል ኮከብ ስትቆጥሪ

እኔ ምስኪኑ

ምን ያገባኛል ስላንቺ ኮከብ
ምን ያገባኛል የእንቅልፍሽ ማጠር
የኔ ችግር ነው ወሰን የሌለው
የኔ ስቃይ ነው  የማይቆጠር

እህት አበባ  ፡ እህት አበባ
እህት አበባ  ስትልሽ ከርማ፤
ጥላሽ ብትሄድም በሀምሌ ጭለማ
እኔ ላይ "አዬዬ".. አትበዪብኝ፡
ለኔ አመቱ ነው  የጨለመብኝ።

ተይ ባለጊዜ..
ተይ እንቁጣጣሽ..
ሀገር ጉድ አቅፈሽ ፥
ሁሌ እየመጣሽ፦

እንኩ አትበዪን፡

ሀዘን ቁስላችን ፡ ድኖ ሳይገግም፤
ካምናው የሚብስ
ሌላ አዲስ አመት ..አንፈልግም!

🔘ሚኪያስ ፈይሳ🔘

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
😢129👏3
መስከረም 2 ቀን 1967 ዓ.ም አፄ ኃይለሥላሴ ከዙፋናቸው የወረዱት 48ተኛ ዓመት!

#ጃንሆይ_ያቺን_ሰዓት!
=============================
መስከረም 2, 1967 ዓ.ም የደርግ አባላት 13 ሆነው ወደ ቤተ-መንግሥት ሄዱና ጃንሆይ የአገዛዝ ዘመናቸው ማብቃቱን አረዷቸው፡፡ የደርግ አባላት ቤተ-መንግሥት ደርሰው ንጉሱን አስጠሯቸው፡፡

ንጉሱም በዝግታ ከፎቅ ላይ ወርደው በዙፋናቸው ላይ ሲቀመጡ የደርግ አባላት ደነገጡ፡፡ ሻምበል ደበላ ዲንሳ ደርግ የወሰነውን የውሳኔ ሃሳብ አነበቡ …

"ለሀገርና ለህዝብ ደህንነት ሲባል በዛሬው ዕለት ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ከስልጣን ወርደዋል፤ ለደህንነትዎ ሲባልም አስተባባሪው ኮሚቴ ወዳዘጋጀልዎ ቦታ እንዲሄዱ ተወስኗል …" የሚል ይዘት ያለው ደብዳቤ አነበቡ፡፡

ሻምበል ደበላ ውሳኔውን አንበበው ሲጨርሱ ንባባቸውን ሲጀምሩ የሰጡትን ወታደራዊ ሰላምታ ደገሙ፡፡ ንጉሱም ዝም ብለው ቆዩና መናገር ጀመሩ፡፡

"ያነበባችሁትን ሰምተናል፤ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገሥት ስንሆን ስም ብቻ አይደለም፡፡ ቢሆንም በየጊዜው የሚለዋወጠው ነገር ደግሞ ላገር የሚጠቅም ነገር እስካለበት…

የኢትዮጵያን ታሪክ ጠብቃችሁ ማልማት ከቻላችሁ የእኛ ታሪክ እዚህ ላይ ያበቃል፤ ካልቻላችሁ የእናንተ ታሪክ ያበቃና የእኛ ይቀጥላል ፤ አገራችንንና ሕዝባችንን በምንችለው አገልግለናል ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ እድል የእኛን መወገድ የሚጠይቅ ከሆነ ስራችንን አቁመን ማንኛውንም ነገር ለመቀበል ዝግጁ ነን፤ ‹አሁን ተራው የእኛ ነው› ካላችሁ ኢትዮጵያን ጠብቁ›› በማለት ተናገሩ፡፡

… ከዚያም ንጉሱ ውብ በሆነችው ሮልስ ሮይስ መኪናቸው ሳይሆን ባረጀች ሰማያዊ ቮልስ ዋገን መኪና ተጭነው ወደ አራተኛ ክፍለ ጦር ግቢ ተወሰዱ፡፡
"ወደ ዋገን ወርደው ሲተኩ በሌላ" እንዲል ቴዲ አፍሮ ሰላም ዋሉ!!
12😢6😱2
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_አራት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///
ስርጉት እኩለ ለሊት ቢያልፍም ኪችን ውስጥ ስራ እየሰራች ስለነበር አልተኛችም..ድንገት ግን የውጭ በራፍ ሲንጎጎ ስትሰማ እጇ ላይ የነበረውን የሸክላ ሰሀን ለቀቀችውን ወለል ላይ አርፎ ፍርክስክስ ብሎ ተሰበረባት፡፡የበሩ መንኳኳት እንደቀጠለ ነው..ቶሎ ብላ ኪችኑን ለቃ ወጣችና ወደሳሎን ሄደች ...

" በፈጣሪ ማን ነው ?" ጠየቀች፡፡

"ስርጉት… እኔ ነኝ ..ክፈቺ."

የሰማችውን ድምፅ ልታምን አልቻለችም  ….ለማሰብ ጥቂት ሰከንድ እንኳን ሳታቅማማ
ተንደርድራ ወደበሩ ሄደችና ከፈተችው፡፡

በረንዳው ላይ ተገትሯል…ለደቂቃዎች በራፉን አንደያዘች በትኩረት ተመለከተች፣

‹‹በሰላም ነው ጁኒዬር?››

‹‹ሰላም ነው››መለሰላት፡፡

‹‹ግባ …››አለችና ከበራፉ ዞር አለችለት..ሰተት ብሎ ገባ፡፡

"እዚህ ምን እየሰራህ ነው?"

"አንቺ ጋር መጥቼ ነዋ…ክብር ዳኛ ተኝቶ እንደሚሆን እገምታለው››

"አዎ አባዬ በጊዜ ነው የተኛው።››

የቀድሞ ባለቤቷ በዚህ እኩለ ለሊት እሷን ብሎ የሚመጣበት አንድም አሳማኝ ምክንያት ሊመጣላት አልቻለም፡፡ ቢሆንም ግን….ግድ አልነበራትም። እዚህ መገኘቱ በቂ ነበር። አባቷ ካገመሰው ቦድካ በብርጭቆ ቀዳችና ሰጠችው፡፡ተቀበላትና በቆመበት አንዴ ተጎነጨለት፡፡

"ይህ የሌሊቱ የመጀመሪያ መጠጥህ አይደለም አይደል?"

"አይ..አይደለም." ድምፁን ዝቅ አድርጎ መለሰላት ፡፡

"ወደእኔ እንድትመጣ ለወራት ስጠብቅ ነበር ። ከዚህ ሁሉ ጊዜ በኋላ አሁን ወደእኔ ስትመጣ ደግሞ ለምን የሚል ጥያቄ በአእምሮዬ እየተመላለሰ ነው፡፡››አለችው፡፡

" ፈልጌ ነበር." አላት፡፡

ለጁኒየር አእምሮ ያ በቂ ምክንያት እንደሆነ ታውቃለች። ሶፋው ላይ ተቀመጠና ጎትቶ ከጎኑ አስቀመጣት።ከበርካታ ደቂቃ ፀጥታ በኋላ " በእርባታ ድርጅቱ ውስጥ ስለተፈጠረው ችግር ሰምቻለሁ" አለችው.

"አሁን ሁሉ ነገር ሰላም ሆኗል….እሳቱ በጊዜው ነው የተደረሰበት…በጣም የከፋ ሊሆን ይችል ነበር."

እያመነታች እጇን እጁ ላይ አሳረፈች፡፡
‹‹አንተ ግን ራስህን ጠብቅ…ንብረታችሁን ለማቃጠል የደፈረ ጠላት በእናንተም ላይ ቀጥታ ጥቃት ከመፈፀም ወደኃላ ላይል ይችላል፡፡››

"አሁንም ለደህንነቴ ትጨነቂያለሽ?"

"ሁልጊዜ።"አለችው፡፡

‹‹ሰሎሜ እንዳንቺ ጣፋጭ ሆኖልኝ አታውቅም። ››

"የደከመህ እና የተቸገርክ ትመስላለህ?።"

"አዎ ደክሞኛል!!።"

ሶፋው ላይ ሙሉ በሙሉ ወጣና ትራሱን ተንተርሶ አረፈ። "በሰሎሜ ግድያ ላይ ያለው ውዥንብር እየበጠበጠን ነው።ሁሉም ነገር እንደ ገሃነም ተስፋ አስቆራጭ ነው።››አላት፡፡ከትራሱ ቀና አለና እሷ ትከሻ ላይ ተንተራሰ"እህ…ጥሩ መዓዛ አለሽ…ይህ ሽታ ናፍቆኝ ነበር. በጣም ንጹህ. ነው፡፡

"ስለዚህ ምርመራ በጣም የሚያስጨንቅህ ምንድን ነው?"

"ምንም የተለየ ነገር የለም። አለም ነች ። እሷ እና እናቴ ዛሬ ተፋጠው ነበር። እናቴ ስለሰሎሜ አንዳንድ መጥፎ ነገሮችን ነገረቻትና በጣም እንድታዝን አደረገቻት… ያ ጥሩ ትእይንት አልነበረም።››

ክንዱ በወገቧ ዙሪያ ላከውና አቀፋት ..እጇን አነሳች እና ጭንቅላቱ ላይ አሳርፋ እንደህፃን ልጅ ታሻሸው ጀመር፡፡

"ዋሻተኋታል እንዴ?"

"የማጣት ፍርሀት የወለደው ውሸት"ጁኒየር ፍላጎት በማጣት አጉተመተመ።

"እናቷ በተገደለችበት ቀን በረንዳ ላይ እንደነበርኩ አልነገርኳትም።ለምን እንደዛ አደረክ ?"

" በተከታታይ ጥያቄዎች እንድታጣድፈኝ አልፈለኩም።አንዳንድ መመለስ የማልችላቸውን ጥያቄዎች ብትጠይቀኝ እንዴት አደርጋለው?›››

‹‹ ጁኒየር ዳግመኛ ችግር ስለፈጠረችብህ ጠላኋት።"

"አለም ሁኔታውን ልትረዳ አትችልም….ያም የእሷ ጥፋት አይደለም.››

ጁኒየር ስለ ሶለሜ ብዙ ጊዜ ተመሳሳይ ነገር ተናግሮ ነበር። የቱንም ያህል ብታበሳጨውም ስለእሷ ጠንከር ያለ ቃል ተናግሮ አያውቅም።ስርጉት በሹክሹክታ

‹‹ይህችን የሰሎሜን ልጅ ልክ እንደእናቷ በጣም እጠላታለሁ››ስትል አንሾካሾከች፡፡

"አሁን ስለዛ አታስቢ። ይህ ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ አያደርግም" አላት፡

እጁን አነሳና እርጥበታማ ከንፈሯ ላይ አሳርፉ ዳበሳት …ከለበሰችው ጋወን ያፈነገጡ ጡቶቾን ተመለከተ።እጁን ከከንፈሯ አነሳና ጡቷ ላይ አስቀመጠ…

‹‹እንደዚህ ሳደርግ ሁል ጊዜ ደስ ይልሽ ነበር ።››

"አሁንም አድርገው።››

‹‹እውነት? ››

"ጡቷን ወደ አፉ አቀረበችለት…ጎረሰው…. እጁን በጭኖቿ መካከል ሰነቀረው፡፡እርጥበት ያለውን ፀጉር እየዳበሰ ወደውስጥ መጓዙን ቀጠለ … ስሙን እየጠራች አቃሰተች።

‹‹ካልፈለግሽ ይገባኛል››አላት

"አይ" አለች በፍጥነት "እፈልጋለው እባክህ።›››ተማፀነችው፡፡፡

"ስርጉቴ ያንቺ በርህራሄ የበለጸገ ፍቅራዊ እንክብካቤ ዛሬ ማታ ያስፈልገኛል። ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ ሁልጊዜም በአንቺ ልተማመንብሽ እችላለሁ።››ሲል ተናዘዘላት፡፡

ጎንበስ አለችና ከንፈሩን ሳመችው፡፡

"ሁልጊዜ ጥሩ ስሜት እንዴሰማኝ እንደጣርሽ ነው…አይደል እንዴ?" ብሎ ጠየቃት፡፡

"አዎ ።"አለችና አጎንብሳ ተመለከተችው። ልክ እንደ መልአክ ፈገግ አለላት ። እንደዚያ ሲያያት ምንም ልትከለክለው አቅም አይኖራትም በጭራሽ።
///
"ወ/ሪት አለም…ወ.ሪት አለም?አለሽ እንዴ?››

አለም ድክምክም ብላ ተኝታ ነበር። ጥገና የተደረገላት በሯን በተደጋጋሚ ሲንኳኳ ነው ከእንቅልፎ የነቃችው፡፡ ስትነቃ… ደንዛዛ እና ቀዝቃዛ ነበር።ከመተኟቷ በፊት ለረጅም ሰዓት ከማልቀሷ የተነሳ ዓይኖቿ አብጠው ነበር።

"ምን ፈለክ?" ድምጿ ለጩኸት የቀረበ ነበር።

" ክፈቺልኝ እትዬ…መልዕክት አለሽ?።"
እንደምንም ከአልጋው ወረደችና ጋወኗን ለብሳ ወደሳሎን በመሄድ በራፉን ከፈተች፡፡የተከራየችበት አፓርታማ ዘበኛ ነው

"እትዬ ስልክሽ ከአገልግሎት መስጫ ውጭ ነው ይላል?"

"አዎ…ዝግ ነው….ለምን ፈለከኝ?" ግራ በመጋባት ጠየቀችው፡፡

‹‹እኔ አይደለውም…አቶ ግርማ የሚባሉ ሰውዬ መጥተው ነበር›› ደነገጠች‹‹የት ነው..?አሁን አለ?››

‹‹አይ ሄደዋል …መልዕክት ንገርልኝ ብለዋል….ነገ ጥቃት ዝዋይ ስብሰባ ስላለ እንድትገኚ ብለዋል››

‹‹ዝዋይ..?የምን ስብሰባ?››

‹‹አላውቅም እትዬ …ሰውዬው ናቸው ያሉት››

‹‹ማለት ተሳስተህ እንዳይሆን?››

‹‹አይ  ይሄው  ማስታወሻ  ላይ  አስፍሬዋለው…››ብሎ  በተወለጋገደ  ፅሁፍ  የተፃፈውን ማስታወሻ አሳያት፡፡

‹‹እሺ በቃ አመሰግናው››ብላ ሸኘችውና ወደ መኝታ ቤቷ ተመለሰች፡፡ከዛ ስልኳን ፈለግችና አበራችው…ዋናው አቃቢ ህጉ ጋር ደወለች….ስልኩ አይሰራም፡፡፡ስልኳን አስቀመጠችና ጋወኗን አውልቃ ቢጃማ መልበስ ጀመረች፡፡እንደጨረሰች ከእንደገና ስልኳን አነሳችና ደወለች፡፡

"ፖሊስ መምሪያ ነው…ምን እንርዳዎት?."

"እባክህ ኩማንደር ገመዶን ፈልጌ ነበር፡፡"

"እሱ የለም። ሌላ የሚረዳሽ ሰው ጋር እናገናኝሽ?"

"አይ፣ አመሰግናለሁ፣ በቀጥታ ከእሱ ጋር መነጋገር አለብኝ…ምክትል አቃቢ ህግ አለም ጎበና ነኝ።"

‹‹ክብርት አቃቢ ህግ እንዴት ነሽ….አሁን የት ነሽ?፧"

"እቤቴ ነኝ …ለምን ጠየቅከኝ?"

"ኩማንደር ወደአንቺ እየመጣ ነው….እስከአሁን ይደርሳል››

‹‹ምነው በሰላም…..?››መልሱን ሳይመልስላት በራፏ ሲንኳኳ ሰማች‹‹ እሺ …በል ደህና ሁን…ደርሶል መሰለኝ ››አለችና ስልኩን በመዝጋት ወደሳሎን ሄዳ በራፉን ከፈተችለት፡፡

‹‹እሺ ኩማንደር ?››

‹‹ዞር በይልኝ እንጂ ልግባ።››

‹‹መግባትህ አስፈላጊ ነው?››እያለች በራፉን ለቀቀችለት፡፡
85👍15