"አይ፣የእናቴ ፍላጎት ነበር፡፡ ያልተፈለገ ባህሪ አንዳለምድ በማለት በውድቀት ለሊት ሻንጣዬንና የትምህርት ቁሳቁሶቼን አሸክማ ወደ አዳሪ ትምህርት ቤት ላከችኝ ።ከስምንተኛ
ክፍል ወደዘጠነኛ ከተዘዋወርኩ በኃላ ግን ጎረመስኩ መሰለኝ..በፍፅም ወደእዛ አዳሪ ትምህር ቤት አልመለሰም ብዬ አመፅኩ ..የአባቴን ድጋፍ አገኘሁና እዚሁ ሻሸመኔ ሀይእስኩል ተመዘገብኩ፡፡››
'"እናትህ ምን አለች?"
" ደስ አላላትም ነበር…በግልፅም ተቃውማ ነበር፡፡በወቅቱ ነገር ግን በወቅቱ በዚህ ጉዳይ ላይ ማድረግ የምትችለው ብዙ ነገር አልነበረም.፡፡አባዬ እኔን በእዚሁ ሀይእስኩል ማስመዝገብ ብቻ ሳይሆን ወደ ከነማው ታዳጊዎች እግር ኳስ ቡድን እንድቀላቀል አጥብቆ ይፈልግ ነበር።በወቅቱ የነበረው አሰልጣኝ ግን እኔ ላይ ብዙም ፍላጎት አላሳየም ነበር፣ ነገር ግን አባዬ ለቡድኑ አዲስ ዩኒፎርም እንደሚገዛ ቃል በመግባት ጉቦ ሰጠው። አሰልጣኙም ተቀበለኝ ፡፡..ጁኒየር እየሳቀ ታሪኩን ቀጠለ ‹‹ስለዚህ ለእግር ኳስ ብድኑ አባል ሆንኩ፡፡ የመጀመርያው የልምምድ ቀን ሊያባረረኝ ተቃርቦ ነበር። ሌሎቹ የቡድኑ አባላትም በእንቅስቃሴዬ ደካማነት ብቻ ሳይሆን በከተማው ውስጥ በጣም ሀብታም የሆነ ሰው ሰውዬ ብቸኛ ወንድ ልጅ በመሆኔ ተበሳጩተውብኝ እንደነበረ አስታውሳለው?"
‹‹እንዴት ተቀበልከው ታዲያ?››
"የሀብታም ልጅ መሆን በጣም ከባድ ስራ ነው፣ ግን አንድ ሰው የግድ ያንን ስራ መስራት አለበት" አለ በሚስብ ፈገግታ። " ለማንኛውም፣ ወደቤት ተመለስኩና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱንም እና እግር ኳስን ቡድኑን በጣም እንደምጠላ ለአባቴ ነገርኩት። እንደ ገመዶ አይነቱን ጉልበተኞች እና ትቢተኛ ወጣቶች ጋር ከመዋል ይልቅ አዳሪትምህረት ቤት ካሉ የገረጡ ትንንሽ ፊት ያላቸውን ደካሞች ጋር መኖር እንደምመርጥ ነገርኩት።"
"በቀጣይ ታዲያ ምን ሆነ፧?"
"እናቴ ራሷን ታማ አለቀሰች። አባቴ በንዴት ራሱን ሳተ። ከዚያም ወደ ውጭ አወጣኝ እና እጆቼ ለመያዝ እስኪዝል ድረስ የኮስ ልምምድ እንዳደርግ አስገደደኝ››
"አስፈሪ ነበር?"
"በእርግጥ አይደለም። ፍላጎቶቼን በልቤ ቀብሬ እንጂ ጥሩ ተጫወች መሆን እፈልግ ነበር ። ባይሳካልኝ እንኳን እዚህ ውጭ መጫወት፣ መብላት፣ መጠጣት እና መተኛት እንዳለብኝ አውቅ ነበር።….መሄድ ትፈልጊያለሽ?"
"አይ፣ ጫወታህን እንድትቀጥል እፈልጋለሁ።" "ይህ መደበኛ ምርመራ ነው እንዴ?"
በቁጣ በታከለበት ፈገግታ።"ውይይት ብንለው ይሻላል" ስትል መለሰችለት፣
"ከዛ በእግር ኳስ ክለቡ ያለህን ተሳትፎ ቀጠልክ ?››ብላ ጀምረው ወደነበረበት የጫወታ ርዕስ መለሰችው፡፡
ጁኒየር ‹‹አዎ፣ እኔ ግን በአንድ ጨዋታ ውስጥ እንኳን አልተጫወትኩም፣ ነበር። ለአውራጃ ሻምፒዮን ሺፕ አልፈን ነበር።"አንገቱን ዝቅ አደረገ እና ፈገግ አለ። ‹‹ከዛ ዋንጫ ጫወታ ቀን ደረሰ…ቡታጅራ ነበር ጫወታው፡፡ቀድመው አገቡብን.. ልንሸነፍ ሆነ … በሰዓቱ ላይ ጥቂት ሰከንዶች ብቻ ቀሩ። ››አሰልጣኙ ወደ ቤንች ሲመለከት እኔን አየ፣ከዛ ስሜን ጮኸ ተጣራ። ከፍራቻዬ የተነሳ በሱሪዬ ላይ መሽናት ነበር የቀረኝ››
"ከዛ እንዴት ሆነ?፧"በጉጉት ጠየቀችው፡፡
እንደምንም እራሴን አጠነካክሬ ቡድኑን ለመቀላቀል ሮጬ ወጣሁ። በሜዳው ላይ ያለው ንጹህ ማሊያ የኔ ብቻ ነው።ገመዶ ሜዳ ውስጥ ነበር" አለም ከጋዜጣ ዘገባዎች ይህን ታውቅ ነበር.
"አዎ የኔ መሲህ። መምጣቴን ሲያይ አቃሰተ፣ እና አሰልጣኙ የነገረኝን የጨዋታ ታክቲክ ለውጥ ስነግረውም ጮክ ብሎ ዓይኖቼን መሀል እያየኝ ኀእንዲህ አለኝ። ፣ ከጎሉ በግራ በክል ሁን ፣ እንደምንም ብዬ ኳሷን ወደአንተ ልካታለው…ወደጎል ለጋት..እርግጠኛ ነህ ታደርገዋለህ››አለኝ…ለአፍታ ጁኒየር ዝም አለ፣ ትዝታ ውስጥ ሰጥሟል።
"የዛን ቀኑን ሁኔታ በህይወት እስካለው ድረስ መቼም አልረሳውም። ከዛ ያገኘነውን ቅጣት ምት ሲመታ ገመዶ እግር ስር ነው ያረፈው …ሁለት ተጫዋቾችን ሸውዶ አለፈና ከእኔ ተሻለ ሁለት አማራጭ እያለው ለእኔ አቀበለኝ……በደመነፍስ ወደጎሉ ላኳት …የተዘናጋውን በረኛ አለፈችና መረብ ላይ አረፈች፡፡ከዛ በኃላ የሆነውን ነገር ምን ብዬ ላስረዳሽ ››
"አባትህ ደስተኛ እንደሚሆን እርግጠኛ ነኝ."
ጁኒየር አንገቱን ወደ ኋላ ነቀነቀና እና እንባ አስኪወጣው ሳቀ ።
"አጥሩን ዘሎ ወንበሩን ጥሎ ወደ ሜዳው ቀረበ ..ሜዳው ውስጥ መግባት ነው የቀረው፡፤
"እናትህስ?"
"እናቴ! የእግር ኳስ ጨዋታ ብትሞት እንኳን ማየት አትፈልግም ።የአረመኔዎች ጫወታ ነው ብላ ታስባለች።ግን ከአባቴ በስተቀር ማንም ስለ እኔ ምን ቢያስብ ግድ አልነበረኝም። በዚያ ምሽት በጣም ነበር የኮራብኝ ።ጥቋቁር አይኖቹ በማስታወስ ያበሩ ነበር።ከዛ በፊት ገመዶን አግኝቶ አያውቅም ነበር፣ ነገር ግን በእለቱ የእግር ኳስ አባላትን እና ሁሉንም አቀፋቸው። ያ ምሽት የጓደኝነታችን መጀመሪያ ነበር። ብዙም ሳይቆይ የገመዶ አባት ሞተ፣ እና ወደ እኛ ቤት መጥቶ እንዲኖር ምክንያት ሆነው ።››
ለተወሰነ ደቂቃ በመሀከላቸው ፀጥታ ሰፈነ….ዝም ብሎ በፅሞና ሲመለከታት ቆየና "ጌታ ሆይ፣ በዚያን ጊዜ የነበረችውን ሰሎሜን ትመስያለሽ" አለ በለሆሳስ። "በባህሪ ብዙ አትመሳሰሉም , ነገር ግን የአንቺ አገላለጽ. ከእርሷ ጋር ተመሳሳይ ነው..በዛ ላይ ሁለታችሁም ተመሳሳይ አይነት የማዳመጥ ጥራት አላችሁ." እጁን ዘርግቶ ፀጉሯን ነካ። "እሷም እንደአንቺ ማዳመጥ ትወድ ነበር።ቢያንስ የሚያወራውን ሰው እደተረዳችው እንዲያስብ ታደርጋዋለች። ዝም ብላ ለሰዓታት ማዳመጥ ትችላለች"
"መጀመሪያ ወደ እሷ የሳበህ ያ ነው?"
" አይ" አለ በሚገርም ፈገግታ። "ወደ እሷ የሳበኝ የመጀመሪያው ነገር ዘጠነኛ ክፍል እያለው የወንድ ልጅ የጉርምስና ምኞት ነበር። ሰሎሜ ለመጀመሪያ ጊዜ በትምህርት ቤት አዳራሽ ውስጥ ሳያት ቀልቤን ነበር የሰለበችው፣ በጣም ቆንጆ ነበረች።"
" አሳደድካት?"
"ሄይ፣ ደንግጬ ነበር እንጂ አላበድኩም።የገመዶ ፍቅረኛ ነበረች" አለ በማያሻማ ሁኔታ።
‹‹ስለዚህ ምንም ጥያቄ አልነበረም››
" ተነሺ። ብንሄድ ይሻለናል:: ብርዱ ኃይለኛ እየሆነ ነው:: በዛ ላይ ጨለማው እየጠነከረ ነው.››
አለም ከተቀመጠችበት ቀድማ ተነሳች…ተክትሏት ተነሳ፡፡"ጁኒየር አበቦቹን ስላመጣህ አመሰግናለሁ."አለችው
"ምንም አይደል።"
"ለእሷ ያላህን ለዘመናት የማይደበዝዝ አሳቢነት አደንቃለሁ."
"በእውነቱ ከሆነ ዛሬ ወደዚህ የመጣሁበት ድብቅ ምክንያት ነበረኝ።" "ወይ?"
"ኡህ-ሁህ" አለ ሁለቱንም እጆቿን በመያዝ" ወደ ቤታችን ለእራት ልጋብዝሽ ነበር››አላት..ሀሳቡ ቀደም ብሎ ያሰበበት ሳይሆን ድንገት የመጣለት ነው፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ክፍል ወደዘጠነኛ ከተዘዋወርኩ በኃላ ግን ጎረመስኩ መሰለኝ..በፍፅም ወደእዛ አዳሪ ትምህር ቤት አልመለሰም ብዬ አመፅኩ ..የአባቴን ድጋፍ አገኘሁና እዚሁ ሻሸመኔ ሀይእስኩል ተመዘገብኩ፡፡››
'"እናትህ ምን አለች?"
" ደስ አላላትም ነበር…በግልፅም ተቃውማ ነበር፡፡በወቅቱ ነገር ግን በወቅቱ በዚህ ጉዳይ ላይ ማድረግ የምትችለው ብዙ ነገር አልነበረም.፡፡አባዬ እኔን በእዚሁ ሀይእስኩል ማስመዝገብ ብቻ ሳይሆን ወደ ከነማው ታዳጊዎች እግር ኳስ ቡድን እንድቀላቀል አጥብቆ ይፈልግ ነበር።በወቅቱ የነበረው አሰልጣኝ ግን እኔ ላይ ብዙም ፍላጎት አላሳየም ነበር፣ ነገር ግን አባዬ ለቡድኑ አዲስ ዩኒፎርም እንደሚገዛ ቃል በመግባት ጉቦ ሰጠው። አሰልጣኙም ተቀበለኝ ፡፡..ጁኒየር እየሳቀ ታሪኩን ቀጠለ ‹‹ስለዚህ ለእግር ኳስ ብድኑ አባል ሆንኩ፡፡ የመጀመርያው የልምምድ ቀን ሊያባረረኝ ተቃርቦ ነበር። ሌሎቹ የቡድኑ አባላትም በእንቅስቃሴዬ ደካማነት ብቻ ሳይሆን በከተማው ውስጥ በጣም ሀብታም የሆነ ሰው ሰውዬ ብቸኛ ወንድ ልጅ በመሆኔ ተበሳጩተውብኝ እንደነበረ አስታውሳለው?"
‹‹እንዴት ተቀበልከው ታዲያ?››
"የሀብታም ልጅ መሆን በጣም ከባድ ስራ ነው፣ ግን አንድ ሰው የግድ ያንን ስራ መስራት አለበት" አለ በሚስብ ፈገግታ። " ለማንኛውም፣ ወደቤት ተመለስኩና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱንም እና እግር ኳስን ቡድኑን በጣም እንደምጠላ ለአባቴ ነገርኩት። እንደ ገመዶ አይነቱን ጉልበተኞች እና ትቢተኛ ወጣቶች ጋር ከመዋል ይልቅ አዳሪትምህረት ቤት ካሉ የገረጡ ትንንሽ ፊት ያላቸውን ደካሞች ጋር መኖር እንደምመርጥ ነገርኩት።"
"በቀጣይ ታዲያ ምን ሆነ፧?"
"እናቴ ራሷን ታማ አለቀሰች። አባቴ በንዴት ራሱን ሳተ። ከዚያም ወደ ውጭ አወጣኝ እና እጆቼ ለመያዝ እስኪዝል ድረስ የኮስ ልምምድ እንዳደርግ አስገደደኝ››
"አስፈሪ ነበር?"
"በእርግጥ አይደለም። ፍላጎቶቼን በልቤ ቀብሬ እንጂ ጥሩ ተጫወች መሆን እፈልግ ነበር ። ባይሳካልኝ እንኳን እዚህ ውጭ መጫወት፣ መብላት፣ መጠጣት እና መተኛት እንዳለብኝ አውቅ ነበር።….መሄድ ትፈልጊያለሽ?"
"አይ፣ ጫወታህን እንድትቀጥል እፈልጋለሁ።" "ይህ መደበኛ ምርመራ ነው እንዴ?"
በቁጣ በታከለበት ፈገግታ።"ውይይት ብንለው ይሻላል" ስትል መለሰችለት፣
"ከዛ በእግር ኳስ ክለቡ ያለህን ተሳትፎ ቀጠልክ ?››ብላ ጀምረው ወደነበረበት የጫወታ ርዕስ መለሰችው፡፡
ጁኒየር ‹‹አዎ፣ እኔ ግን በአንድ ጨዋታ ውስጥ እንኳን አልተጫወትኩም፣ ነበር። ለአውራጃ ሻምፒዮን ሺፕ አልፈን ነበር።"አንገቱን ዝቅ አደረገ እና ፈገግ አለ። ‹‹ከዛ ዋንጫ ጫወታ ቀን ደረሰ…ቡታጅራ ነበር ጫወታው፡፡ቀድመው አገቡብን.. ልንሸነፍ ሆነ … በሰዓቱ ላይ ጥቂት ሰከንዶች ብቻ ቀሩ። ››አሰልጣኙ ወደ ቤንች ሲመለከት እኔን አየ፣ከዛ ስሜን ጮኸ ተጣራ። ከፍራቻዬ የተነሳ በሱሪዬ ላይ መሽናት ነበር የቀረኝ››
"ከዛ እንዴት ሆነ?፧"በጉጉት ጠየቀችው፡፡
እንደምንም እራሴን አጠነካክሬ ቡድኑን ለመቀላቀል ሮጬ ወጣሁ። በሜዳው ላይ ያለው ንጹህ ማሊያ የኔ ብቻ ነው።ገመዶ ሜዳ ውስጥ ነበር" አለም ከጋዜጣ ዘገባዎች ይህን ታውቅ ነበር.
"አዎ የኔ መሲህ። መምጣቴን ሲያይ አቃሰተ፣ እና አሰልጣኙ የነገረኝን የጨዋታ ታክቲክ ለውጥ ስነግረውም ጮክ ብሎ ዓይኖቼን መሀል እያየኝ ኀእንዲህ አለኝ። ፣ ከጎሉ በግራ በክል ሁን ፣ እንደምንም ብዬ ኳሷን ወደአንተ ልካታለው…ወደጎል ለጋት..እርግጠኛ ነህ ታደርገዋለህ››አለኝ…ለአፍታ ጁኒየር ዝም አለ፣ ትዝታ ውስጥ ሰጥሟል።
"የዛን ቀኑን ሁኔታ በህይወት እስካለው ድረስ መቼም አልረሳውም። ከዛ ያገኘነውን ቅጣት ምት ሲመታ ገመዶ እግር ስር ነው ያረፈው …ሁለት ተጫዋቾችን ሸውዶ አለፈና ከእኔ ተሻለ ሁለት አማራጭ እያለው ለእኔ አቀበለኝ……በደመነፍስ ወደጎሉ ላኳት …የተዘናጋውን በረኛ አለፈችና መረብ ላይ አረፈች፡፡ከዛ በኃላ የሆነውን ነገር ምን ብዬ ላስረዳሽ ››
"አባትህ ደስተኛ እንደሚሆን እርግጠኛ ነኝ."
ጁኒየር አንገቱን ወደ ኋላ ነቀነቀና እና እንባ አስኪወጣው ሳቀ ።
"አጥሩን ዘሎ ወንበሩን ጥሎ ወደ ሜዳው ቀረበ ..ሜዳው ውስጥ መግባት ነው የቀረው፡፤
"እናትህስ?"
"እናቴ! የእግር ኳስ ጨዋታ ብትሞት እንኳን ማየት አትፈልግም ።የአረመኔዎች ጫወታ ነው ብላ ታስባለች።ግን ከአባቴ በስተቀር ማንም ስለ እኔ ምን ቢያስብ ግድ አልነበረኝም። በዚያ ምሽት በጣም ነበር የኮራብኝ ።ጥቋቁር አይኖቹ በማስታወስ ያበሩ ነበር።ከዛ በፊት ገመዶን አግኝቶ አያውቅም ነበር፣ ነገር ግን በእለቱ የእግር ኳስ አባላትን እና ሁሉንም አቀፋቸው። ያ ምሽት የጓደኝነታችን መጀመሪያ ነበር። ብዙም ሳይቆይ የገመዶ አባት ሞተ፣ እና ወደ እኛ ቤት መጥቶ እንዲኖር ምክንያት ሆነው ።››
ለተወሰነ ደቂቃ በመሀከላቸው ፀጥታ ሰፈነ….ዝም ብሎ በፅሞና ሲመለከታት ቆየና "ጌታ ሆይ፣ በዚያን ጊዜ የነበረችውን ሰሎሜን ትመስያለሽ" አለ በለሆሳስ። "በባህሪ ብዙ አትመሳሰሉም , ነገር ግን የአንቺ አገላለጽ. ከእርሷ ጋር ተመሳሳይ ነው..በዛ ላይ ሁለታችሁም ተመሳሳይ አይነት የማዳመጥ ጥራት አላችሁ." እጁን ዘርግቶ ፀጉሯን ነካ። "እሷም እንደአንቺ ማዳመጥ ትወድ ነበር።ቢያንስ የሚያወራውን ሰው እደተረዳችው እንዲያስብ ታደርጋዋለች። ዝም ብላ ለሰዓታት ማዳመጥ ትችላለች"
"መጀመሪያ ወደ እሷ የሳበህ ያ ነው?"
" አይ" አለ በሚገርም ፈገግታ። "ወደ እሷ የሳበኝ የመጀመሪያው ነገር ዘጠነኛ ክፍል እያለው የወንድ ልጅ የጉርምስና ምኞት ነበር። ሰሎሜ ለመጀመሪያ ጊዜ በትምህርት ቤት አዳራሽ ውስጥ ሳያት ቀልቤን ነበር የሰለበችው፣ በጣም ቆንጆ ነበረች።"
" አሳደድካት?"
"ሄይ፣ ደንግጬ ነበር እንጂ አላበድኩም።የገመዶ ፍቅረኛ ነበረች" አለ በማያሻማ ሁኔታ።
‹‹ስለዚህ ምንም ጥያቄ አልነበረም››
" ተነሺ። ብንሄድ ይሻለናል:: ብርዱ ኃይለኛ እየሆነ ነው:: በዛ ላይ ጨለማው እየጠነከረ ነው.››
አለም ከተቀመጠችበት ቀድማ ተነሳች…ተክትሏት ተነሳ፡፡"ጁኒየር አበቦቹን ስላመጣህ አመሰግናለሁ."አለችው
"ምንም አይደል።"
"ለእሷ ያላህን ለዘመናት የማይደበዝዝ አሳቢነት አደንቃለሁ."
"በእውነቱ ከሆነ ዛሬ ወደዚህ የመጣሁበት ድብቅ ምክንያት ነበረኝ።" "ወይ?"
"ኡህ-ሁህ" አለ ሁለቱንም እጆቿን በመያዝ" ወደ ቤታችን ለእራት ልጋብዝሽ ነበር››አላት..ሀሳቡ ቀደም ብሎ ያሰበበት ሳይሆን ድንገት የመጣለት ነው፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
YouTube
አትሮኖስ_ Tube
Share your videos with friends, family, and the world
❤32👍25
#ይናፍቀኝ_ነበር
ዞሮ ዞሮ ከቤት
ይላል የኛ ተረት ::
አቧራው ፀሃዩ ይናፍቀኝ ነበር፤
አፈሩ ጠጠሩ ይናፍቀኝ ነበር::
የመንደር ጭስ ማታ…….
ይናፍቀኝ ነበር የሳር ቤት ጥቀርሻው
መደቡ ምሰሶው፤
ማገሩ ግድግዳው፤ አጥሩና ጥሻው::
የፈራረሰ ካብ………
ቀጭን ጠባብ መንገድ በመንደር የሚሮጥ፤
ቅጠል የሸፈነው፡
ሳር ያለባበሰው፤
እነዚህ እነዚህ ይናፍቁኝ ነበር፤
የተቆላ ቡና ፤
የሚወቀጥ ቡና፤
የጎረቤት ቡና አቦል ሁለተኛ፤
የተረጨ ቆሎ የሚያርቅ መጋኛ፤
የሚጨሰው ዕጣን………
እንጀራ በመሶብ ወጥ የፈሰሰበት
ያገልግል እንጀራ፤ የሚቧጠጥ ፍትፍት፤
የክክ ወጥ የሽሮ፤
የስጋ የዶሮ፡፡
ይናፍቀኝ ነበር ቅራሪ ጉሽ ጠላ፤
ይናፍቀኝ ነበር ፊልተር ዞማ ኮላ፡፡
ያገራችን ድግስ……..
ከበሮው ጭፈራው፤
ዝላዩ እስክስታው፤ ስካሩ ሁካታው፡፡
ትርክምክሙ ነገር ግፍያው ትንቅንቁ፤
ኳኳታው እርግጫው ዘፈን ድብልቅልቁ፡፡
“አሸወይና ወይና“
“እስቲ እንደ ጎጃሞች“
“አሲዮ ቤሌማ… ኦሆሆ አሀሀ…"
የቄስ ትምህርት ቤት
የህፃናቱ ድምፅ፤
“ሀ...ሁ…ሂ…ሃ…“ ዜማ ነበር የናፈቀኝ
የጽጌ ጭፈራ ነበር የናፈቀኝ፡፡
ከበሮ ፅናፅል፤
ሆሳዕና ጥምቀት፤
ፋሲካ ገና ሁዳዴና ስግደት፤
ቡሄ ሆያ ሆዬ፤
የእስላሞች አረፋ የኦሮሞች ሸጎዬ፤
የቁልቢ ገብርዔል፤
ልደታ፤
ፍልሰታ፡፡
ዕንቁጣጣሽ ነበር መስከረም ሲጠባ፤
አውቆ የበቀለ ወፍ ዘራሽ አበባ፡፡
ለምለም አረንጓዴ…
ያልተጠበቀ መስክ ከብት የሚግጥበት፤
የደመና ግላጭ የሚጫወትበት፡፡
ሌላም ብዙ ነበር…
ሌላም ….ደግሞ ሌላ…..፡፡
ያገሬ ሰው ነበር እኔን የናፈቀኝ፤
ጠይም ቆዳ ነበር እኔን የናፈቀኝ፤
ቀይ ዳማ ነበር ጥቁር ቆዳ ነበር፤
ቁርንጫጭ ከርዳዳ፤ ዞማ ጠጉር ነበር፤
ያገራችን ቋንቋ…
ያገሬ ሙዚቃ ያገራችን ዜማ፤
ጥበብ እጀ ጠባብ ያገራችን ሸማ፤
ነበረ ናፍቆቴ ለሁሉም…
ለሁሉ፡፡
ለሸዋ፤ ለወሎ፤ ለትግሬ፤ በጌ ምድር፤
ለጎጃም ወለጋ፤ አሩሲ ኢሉባቡር፤
ኤርትራ ገሙጎፋ፤
ሲዳሞና ከፋ፡፡
ለሁሉም ለሁሉ ነበረ ናፍቆቴ፤
አለብኝ ትዝታ
ዘመዶቼ ሳሙኝ፤
ጓደኞቼም ጋብዙኝ፤
ሊስትሮ ጨብጠኝ::
ባለጋሪ ንዳ መንደሩን አሳየኝ፤
ያገሬ ልጅ ቆንጆ “ቤት ለእንግዳ በዪኝ“፡፡
አለብኝ ትዝታ…..
አዲስ አበባ ላይ ነበረ ናፍቆቴ
መናገሻ ነበር፤ እንጦጦ ነበረ፤
ኤረር ጋራ ነበር፤ ዝቋላ ነበረ፤
ጃን ሜዳ ነበረ፤ ኮተቤ ነበረ፤
ገፈርሳ ነበረ፤ ጉለሌ ነበረ፤
አዲሱ ከተማ…
“መርካቶ ዲጂኖ ችምችም ያለው መንደር“
ከተማው እንብርት ደጃች ውቤ ሰፈር
የቸርችል ጎዳና፤
የባቡሩ ጣቢያ፤
ቢሾፍቱ ነበረ፤ ናዝሬት፤ ሞጆ አዋሽ::
ድሬዳዋ ነበር፤
ዓለምማያ ነበር::
ሐረርጌ ነበረ የተወለድኩበት
እናትና አባቴን ጥዬ የሄድኩበት::
የሚካዔል ጓሮ…
ሐረርጌ ነበረ፡፡
ዞሮ ዞሮ ከቤት…
አገሬ ነበረ እኔን የናፈቀኝ::
ኢትዮጵያ ነበረች
🔘ገብረክርስቶስ ደስታ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ዞሮ ዞሮ ከቤት
ይላል የኛ ተረት ::
አቧራው ፀሃዩ ይናፍቀኝ ነበር፤
አፈሩ ጠጠሩ ይናፍቀኝ ነበር::
የመንደር ጭስ ማታ…….
ይናፍቀኝ ነበር የሳር ቤት ጥቀርሻው
መደቡ ምሰሶው፤
ማገሩ ግድግዳው፤ አጥሩና ጥሻው::
የፈራረሰ ካብ………
ቀጭን ጠባብ መንገድ በመንደር የሚሮጥ፤
ቅጠል የሸፈነው፡
ሳር ያለባበሰው፤
እነዚህ እነዚህ ይናፍቁኝ ነበር፤
የተቆላ ቡና ፤
የሚወቀጥ ቡና፤
የጎረቤት ቡና አቦል ሁለተኛ፤
የተረጨ ቆሎ የሚያርቅ መጋኛ፤
የሚጨሰው ዕጣን………
እንጀራ በመሶብ ወጥ የፈሰሰበት
ያገልግል እንጀራ፤ የሚቧጠጥ ፍትፍት፤
የክክ ወጥ የሽሮ፤
የስጋ የዶሮ፡፡
ይናፍቀኝ ነበር ቅራሪ ጉሽ ጠላ፤
ይናፍቀኝ ነበር ፊልተር ዞማ ኮላ፡፡
ያገራችን ድግስ……..
ከበሮው ጭፈራው፤
ዝላዩ እስክስታው፤ ስካሩ ሁካታው፡፡
ትርክምክሙ ነገር ግፍያው ትንቅንቁ፤
ኳኳታው እርግጫው ዘፈን ድብልቅልቁ፡፡
“አሸወይና ወይና“
“እስቲ እንደ ጎጃሞች“
“አሲዮ ቤሌማ… ኦሆሆ አሀሀ…"
የቄስ ትምህርት ቤት
የህፃናቱ ድምፅ፤
“ሀ...ሁ…ሂ…ሃ…“ ዜማ ነበር የናፈቀኝ
የጽጌ ጭፈራ ነበር የናፈቀኝ፡፡
ከበሮ ፅናፅል፤
ሆሳዕና ጥምቀት፤
ፋሲካ ገና ሁዳዴና ስግደት፤
ቡሄ ሆያ ሆዬ፤
የእስላሞች አረፋ የኦሮሞች ሸጎዬ፤
የቁልቢ ገብርዔል፤
ልደታ፤
ፍልሰታ፡፡
ዕንቁጣጣሽ ነበር መስከረም ሲጠባ፤
አውቆ የበቀለ ወፍ ዘራሽ አበባ፡፡
ለምለም አረንጓዴ…
ያልተጠበቀ መስክ ከብት የሚግጥበት፤
የደመና ግላጭ የሚጫወትበት፡፡
ሌላም ብዙ ነበር…
ሌላም ….ደግሞ ሌላ…..፡፡
ያገሬ ሰው ነበር እኔን የናፈቀኝ፤
ጠይም ቆዳ ነበር እኔን የናፈቀኝ፤
ቀይ ዳማ ነበር ጥቁር ቆዳ ነበር፤
ቁርንጫጭ ከርዳዳ፤ ዞማ ጠጉር ነበር፤
ያገራችን ቋንቋ…
ያገሬ ሙዚቃ ያገራችን ዜማ፤
ጥበብ እጀ ጠባብ ያገራችን ሸማ፤
ነበረ ናፍቆቴ ለሁሉም…
ለሁሉ፡፡
ለሸዋ፤ ለወሎ፤ ለትግሬ፤ በጌ ምድር፤
ለጎጃም ወለጋ፤ አሩሲ ኢሉባቡር፤
ኤርትራ ገሙጎፋ፤
ሲዳሞና ከፋ፡፡
ለሁሉም ለሁሉ ነበረ ናፍቆቴ፤
አለብኝ ትዝታ
ዘመዶቼ ሳሙኝ፤
ጓደኞቼም ጋብዙኝ፤
ሊስትሮ ጨብጠኝ::
ባለጋሪ ንዳ መንደሩን አሳየኝ፤
ያገሬ ልጅ ቆንጆ “ቤት ለእንግዳ በዪኝ“፡፡
አለብኝ ትዝታ…..
አዲስ አበባ ላይ ነበረ ናፍቆቴ
መናገሻ ነበር፤ እንጦጦ ነበረ፤
ኤረር ጋራ ነበር፤ ዝቋላ ነበረ፤
ጃን ሜዳ ነበረ፤ ኮተቤ ነበረ፤
ገፈርሳ ነበረ፤ ጉለሌ ነበረ፤
አዲሱ ከተማ…
“መርካቶ ዲጂኖ ችምችም ያለው መንደር“
ከተማው እንብርት ደጃች ውቤ ሰፈር
የቸርችል ጎዳና፤
የባቡሩ ጣቢያ፤
ቢሾፍቱ ነበረ፤ ናዝሬት፤ ሞጆ አዋሽ::
ድሬዳዋ ነበር፤
ዓለምማያ ነበር::
ሐረርጌ ነበረ የተወለድኩበት
እናትና አባቴን ጥዬ የሄድኩበት::
የሚካዔል ጓሮ…
ሐረርጌ ነበረ፡፡
ዞሮ ዞሮ ከቤት…
አገሬ ነበረ እኔን የናፈቀኝ::
ኢትዮጵያ ነበረች
🔘ገብረክርስቶስ ደስታ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤10🔥1🥰1
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለደብረ ታቦር በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
#ቦሔ_አምላክ_አለ
ከተወለድኩበት፥በመንገዴ የዋለ፤
ቦሔ አምላክ አለ።
ቢጎድል እንኳ፥በሱ እምነቴ፤
በምህረቱ፦
ደብረታቦር ሆኗል ቤቴ።
(ብርሀኑ አለ በህይወቴ!)
.
.
.
ከእምነቴ ብጎድልበት፤
ከቤቴ ደጅ፦
ንጉስ ሳኦል፥ባይመጣበት፤
ባርቅ፦ድል ባይነሳበት፤
ብርሀን አርጓል በቤቴ ላይ፦
ክብሩን ገልጧል፥በኔ ህይወት!
ቦሔ አምላክ አለ
.
.
.
ሰማርያ አውራጃ፥ባልሆንም እረኛ፤
ፅድቄ ባይመዝንም፦
ብርሀኑን ለማየት፥ባልሆንም ተረኛ፤
ብርሀኑን ሲገልጥ፦
ቀን ነው ብዬ፥የምጠብቅ፤
ወላጆቼ ባይፈልጉኝ፥ባያመጡ ሙልሙል ለስንቅ፤
የኔ ነገር፥ቢሆን ወረት፤
ክብሩን ገልጧል፥በኔ ህይወት!
(ብርሀን አርጓል፥በኔ ህይወት!)
🔘ሃይማኖት ሹመት 🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
#ቦሔ_አምላክ_አለ
ከተወለድኩበት፥በመንገዴ የዋለ፤
ቦሔ አምላክ አለ።
ቢጎድል እንኳ፥በሱ እምነቴ፤
በምህረቱ፦
ደብረታቦር ሆኗል ቤቴ።
(ብርሀኑ አለ በህይወቴ!)
.
.
.
ከእምነቴ ብጎድልበት፤
ከቤቴ ደጅ፦
ንጉስ ሳኦል፥ባይመጣበት፤
ባርቅ፦ድል ባይነሳበት፤
ብርሀን አርጓል በቤቴ ላይ፦
ክብሩን ገልጧል፥በኔ ህይወት!
ቦሔ አምላክ አለ
.
.
.
ሰማርያ አውራጃ፥ባልሆንም እረኛ፤
ፅድቄ ባይመዝንም፦
ብርሀኑን ለማየት፥ባልሆንም ተረኛ፤
ብርሀኑን ሲገልጥ፦
ቀን ነው ብዬ፥የምጠብቅ፤
ወላጆቼ ባይፈልጉኝ፥ባያመጡ ሙልሙል ለስንቅ፤
የኔ ነገር፥ቢሆን ወረት፤
ክብሩን ገልጧል፥በኔ ህይወት!
(ብርሀን አርጓል፥በኔ ህይወት!)
🔘ሃይማኖት ሹመት 🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
YouTube
አትሮኖስ_ Tube
Share your videos with friends, family, and the world
❤6👍4
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ጁኒዬር አለምን ይዞ ወደ ወላጆቹ ቤት ሲደርስ ሳሎን ያለው አባቱ ብቻ ነው፡፡አቶ ፍሰሀ ከመቀመጫቸው ተነስተው እጇን እየጨበጡ"ጁኒየር ስላገኘሽ እና እንድትመጪም ስላሳመነሽ ደስ ብሎኛል" አላት፡፡
"እኔም እዚህ በመሆኔ ደስተኛ ነኝ።"
"ደህና….ተቀመጪ››
ተቀመጠች፡፡
"ምን ትጠጫለሽ?"ሲል ጁኒዬር ጠየቃት፡፡ "ነጭ ወይን ካለ ደስ ይለኛል…. እባክህ" አለች.
አቶ ፍሰሀ በጥቋቁር አይኖቹ ትኩር ብሎ እያያት "ነጭ ወይን,? እንዳጋጣሚ ባለቤቴም የነጭ ወይን አፍቃሪ ስለሆነች ከእኛ ቤት ጠፍቶ አያውቅም… አሁን ትመጣና ትቀላለናለች
፡፡››አላት
ጁኒየር መጥሪያውን ሲጫን የቤቱ አገልጋይ ከውስጠኛው ክፍል እየሮጠች መጣች…ነጭ ወይን አምጥታ ለአለም እንድትቀዳላት አዘዛት፡፡ወይኑ መጣና ተቀዳላት..አቶ ፍሰሀና ልጃቸው ጁኒዬር ቢራ ያዙ፡፡
‹‹ጁኒዬር ወደቤት ይዞሽ እንዲመጣ ጠይቄው ነበር..እንዲህ በፍጥነት ይሳካለታል አላልኩም ነበር፡፡››
አለም ግራ ተገባች..እናም ወደ ጁኒዬር ዞር ብላ‹‹ወደእዚህ እንድመጣ ያንተ ፍላጎት መስሎኝ ነበር እኮ››
‹‹እሱማ የእኔም ፍላጎት ነው››አላት በእፍረት አንገቱን አቀርቅሮ፡፡ አለምም ወደ ፍሰሀ ዞራ "እሺ ለምን ነበር የፈለከኝ?"አለችው፡፡
በእሷ ቀጥተኛነት ለጊዜው ያልተደሰተ ይመስላል፣ ቢሆን እሱም በተመሳሳይ መንገድ መለሰላት
"ጠላቶች እንድንሆን… አንቺን በደንብ ማወቅ እፈልጋለሁ።"አላት፡፡
"እኔም የመጣሁት ለዚህ ነው አቶ ፍሰሀ።"አለችው ፍርጥም ብላ፡፡
እሷን ትንሽ ጊዜ ወስዷ ሊያጠናት ሞከረ። "እንዴት ጠበቃ ለመሆን ፈለግሽ?"የተለመደ ግን ደግሞ ድንገተኛ ጥያቄ ጠየቃት፡፡
"የእናቴን ግድያ ለመመርመር ወንጀለኛውን ለፍርድ ለማቅረብ እንድችል.››
መልሱ በድንገት ወደ ከንፈሮቿ የመጣ ነው፣ ይህም መልሷ እንሱን ብቻ ሳይሆን አለምን እራሷን አስገርሟታል። እሷ ከዚህ በፊት የእናቷን ገዳይ መፈለግ ዋና ግቧ እንደሆነ ተናግራ አታውቅም።በዚህ የእናቷ ግድያ ወንጀል ላይ እሷ ራሷም በአያቷ ዘንድ ይፋዊ ተጠርጣሪ ሆና መቅረቧ ነገሩን በቁርጠኝነት እንድትይዘው ገፊ ምክንያት ሆኗታል፡፡ በመጨረሻ ሞት አፋፍ ላይ የምትገኝ አያቷ ለእናቷ ሞት ዋና ተጠያቂ እሷ እንደሆንች በግልፅ ቃል ደጋግማ ነግራታለች።አያቷ የተናገረችው ስህተት እንደሆነ የሚያረጋግጥ ሌላ ማስረጃ እስካላገኘች ድረስ ጥፋቱን እስከ ህይወቷ ድረስ ይዛ ለመኖር ትገደዳለች ። እና አሁን ከሻሸመኔ ከተማ ሃያሎቹ ጋር ተፋጣ የምትገኝት ዋና ምክንያት ራሷን ነፃ ለማውጣት ነው፡፡
አቶ ፍሰሀ "ባል የለሽም? ልጆችስ?"ሲል ሌላ ጥያቄ ጠየቃት፡፡
"አይ የለኝም።
" "ለምን?"
"አባ" አለ ጁኒየር በአባቱ እፍረት ማጣት አፍሮ ‹‹አለም ልተዝናና እንጂ በጥያቅህ እንድታጨናንቃት ይዣት አልመጣሁም››
" ጁኒየር ምንም ችግር የለውም። ይህ የተለመደ ጥያቄ ነው።"አለች አለም፡፡
" እሺ እንደዛ ካልሽ መልስሽ ምንድነው?"አቶ ፍሰሀ ጠየቃት፡፡
"ጊዜ ወይም ዝንባሌ የለኝም."
"በዚህ በእኛ አካባቢም ተመሳሳይ ብዙ ጊዜ እና በቂ ዝንባሌ የለንም."
ጁኒየር በጠወለገ እይታ አባቱን ተመለከተው።የተነገረው አሽሙር እሱን የሚመለከት እንደሆነ ያውቃል"አባዬ የከሸፉብኝን ትዳሮቼን እየጠቀሰ ነው።››በማለት አብራራላት፡፡
"ጋብቻዎች? ስንት ነበሩ?"አለም በጉጉት ጠየቀች
"ሶስት" በማለት ተናዘዘ።
"እና አንዳቸውም እኔን አያት የማድረግ ፍላጎቱም ሆነ ብቃት አልነበራቸውም››አቶ ፍሰሀ ዋና ቅሬታውን ተናገረ፡፡
በዚህ መካከል ከፎቁ ወደታች የሚወርድ የጫማ ኳኳታ ሰሙና በተመሳሳይ ሦስቱም ዞሩ። አንዲት ሴት በተከፈተው በር ላይ ቆማ ነበር። አለም የአቶ ፍሰሀ ሚስት እና የጁኒዬር እናት መሆኗን አወቀች። ከእግር ጥፍሯ እስከ ራስ ፀጉሯ ድረስ ምን እንደምትመስል አእምሮአዊ ምስል ቀርጾ ነበር። ወይዘሮዋ ግን የአለምን አእምሮአዊ ምስል ተቃራኒ ነበረች።
ጁኒዬር እናቴ ጀማይካዊት ነች ስላላት..የሆነች ፈርጣም ..ጠቆር ያለች.. ከንፈረ ትልልቅ…የፀጉሯ ድሬድ መቀመጫዋን የሚነካ አይነት አድርጋ ነበር የሳለቻት…እሷ ግን ቅንጥስጥስ ያለች ቀጭን…ቀይ ቆንጆ ግን ደግሞ ስልችት ያለው ፊት ያየዘች…ሀበሻ መሳይ
ሴት ነች፡፡ጁኒዬር ያንን አፍዛዣ መሳይ ውበቱን እና ለስላሳ ባህሪውን ከማን እንደወረሰው አሁን በግልፅ ገባት ፡፡
"ሃኒ ይህቺ አለም ጎበና ነች" አለ አቶ ፍሰሀ ።
የጁኒዬር እናት ባለቤቷን ችላ ብላ ፈካ ያለ ፊቷ አብርቶ ቀጥ ያለ ቀጭን ከንፈሯ ወደቀኝ በመጠምዘዝ ‹‹አለም ወደቤታችን እንኳን በሰላም መጣሽ…ሳራ እባላለው..የጁኒዬር እናት ነኝ
››አለችና ወንበር ስባ ተቀመጠች፡፡
አለም ከሴትዬዋ ንግግር የፍሰሀ ባለቤት ከመሆኗ በላይ የጁኒዬር እናት በመሆኗ ኩራት እንደሚሰማት ነው የተረዳችው፡፡
"አመሰግናለሁ።"ስትል መለሰች፡፡
ጁኒየር ከተቀመጠበት ተነሳና አንድ ብርጭቆ ነጭ ወይን ቀዳና ለእናቱ አቀበላት.. ። በሚያብረቀርቅ ፈገግታ‹‹አመሰግናለው የእኔ ልጅ››በማለት ተቀበለችው፡፡
እሱም ጎንበስ ብሎ እናቱን የለሰለሰ ስርጉድ ጉንጯን ሳመ። "ራስ ምታትሽ እንዴት ነው?"
"ሙሉ በሙሉ አልተወኝም፣ ነገር ግን እንቅልፍ ረድቶኛል። ስለጠየቅከኝ አመሰግናለሁ።"
አለም የሴትዬዋን እጇች ስታይ ተገረመች …እጇ ነጭ ሲሆኑ … በአውሎ ንፋስ እንደተመታ አበባ በቀላሉ ተሰባሪ ይመስላል።
ባሏን " መቼስ ስለከብቶችና ፈረሶች እያወራህ እያሰለቸሀት ነው አይደል?"አለችው፡፡
"በራሴ ቤት ውስጥ፣ ስለምንስ ባወራ አንቺን ምን ጨነቀሽ?" አቶ ፍሰሀ ቱግ አለ፡፡ ጁኒየር ንግግራቸውን ከዛ በላይ እንዳይጠነክርና አለም ፊት እንዳያሳፍሩን ፈጠን ብሎ ጣልቃ ገባ፡፡
"እማዬ ስለ እርባታ አይደለም እያወራን ያለነው ። አባዬ ከሚስቶቼ ወራሽ የሚሆን ልጅ ለመውለድ ባለመቻሌ እየወቀሰኝ ነበር።"ሲል አብራራላት፡፡
"ጊዜው ሲደርስ ከትክክለኛ ሴት ጋር ልጆች ትወልዳለህ››.አለችና ወደ አለም ዘወር ብላ ጠየቀች፡- “ወ.ሪት አለም በፍፁም አላገባሁም ስትይ ሰምቻለሁ ልበል ?” ብላ ጠየቀችው።
"ልክ ነው"
"እንግዳ ነገር ነው…ቢያንስ የወንድ ጓደኛ ሊኖርሽ ይገባ ነበር፡፡››
"አለም የወንድ ጓደኛ የለኝም አላለችም እኮ
››ጁኒየር አስተካከላት. "በቃ መራጭ ነች"ሲል አከለበት፡፡
"አዎ ከጋብቻ እና ቤተሰብ ከመመሥረት ይልቅ ሙያዬን መርጫለሁ።ለጊዜው፣ ለማንኛውም ነገር ጊዜ የለኝም። ግን እናቴ የሆነ ሙያ ባለቤት ለመሆን ፍላጎት እንዳላት ገልጻ ታውቃለች?"
"እሷን እስከማውቃት ድረስ እንደዛ አይነት ምኞት አልነበራትም" ሲል ጁኒየር መለሰ፣ አለም በፀፀት ስሜት "በጣም ቀድማ በልጅነቷ ነበር የወለደችኝ" አለች።
"ምናልባት ያለዕድሜ ጋብቻ ውስጥ መግባቷ እና ልጅ መውለዷ ወደ ሥራ እንዳትገባ አግዷት ይሆናል….ሰሎሜ የራሷን ምርጫ ነው ተግባራዊ ያደረገችው."ሲል መለሰላት፡፡
"የምታውቀውን ስለነገርከኝ አመሰግናለሁ.››
‹‹ አንድ ጊዜ እኔ እሷና ጀማል ለመዝናናት ወደወንዶ ገነት ሄደን ነበር፡፡በፍል ውሀ ስንታጠብና ስንዋኝ ከዋልን በኃላ በጣም ደክሞን ዛፍ ጥላ ስር ሳሩ ላይ ተዘርረን ሰማዩን አንጋጠን ስለ ምኞታችን ስናወራ እንደነበር ትዝ ይለኛል…ሁላችንም የዋና ልብስ ብቻ ነበር የለበስነው…እና እሷም በመሀላችን ተኝታ ነበር፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ጁኒዬር አለምን ይዞ ወደ ወላጆቹ ቤት ሲደርስ ሳሎን ያለው አባቱ ብቻ ነው፡፡አቶ ፍሰሀ ከመቀመጫቸው ተነስተው እጇን እየጨበጡ"ጁኒየር ስላገኘሽ እና እንድትመጪም ስላሳመነሽ ደስ ብሎኛል" አላት፡፡
"እኔም እዚህ በመሆኔ ደስተኛ ነኝ።"
"ደህና….ተቀመጪ››
ተቀመጠች፡፡
"ምን ትጠጫለሽ?"ሲል ጁኒዬር ጠየቃት፡፡ "ነጭ ወይን ካለ ደስ ይለኛል…. እባክህ" አለች.
አቶ ፍሰሀ በጥቋቁር አይኖቹ ትኩር ብሎ እያያት "ነጭ ወይን,? እንዳጋጣሚ ባለቤቴም የነጭ ወይን አፍቃሪ ስለሆነች ከእኛ ቤት ጠፍቶ አያውቅም… አሁን ትመጣና ትቀላለናለች
፡፡››አላት
ጁኒየር መጥሪያውን ሲጫን የቤቱ አገልጋይ ከውስጠኛው ክፍል እየሮጠች መጣች…ነጭ ወይን አምጥታ ለአለም እንድትቀዳላት አዘዛት፡፡ወይኑ መጣና ተቀዳላት..አቶ ፍሰሀና ልጃቸው ጁኒዬር ቢራ ያዙ፡፡
‹‹ጁኒዬር ወደቤት ይዞሽ እንዲመጣ ጠይቄው ነበር..እንዲህ በፍጥነት ይሳካለታል አላልኩም ነበር፡፡››
አለም ግራ ተገባች..እናም ወደ ጁኒዬር ዞር ብላ‹‹ወደእዚህ እንድመጣ ያንተ ፍላጎት መስሎኝ ነበር እኮ››
‹‹እሱማ የእኔም ፍላጎት ነው››አላት በእፍረት አንገቱን አቀርቅሮ፡፡ አለምም ወደ ፍሰሀ ዞራ "እሺ ለምን ነበር የፈለከኝ?"አለችው፡፡
በእሷ ቀጥተኛነት ለጊዜው ያልተደሰተ ይመስላል፣ ቢሆን እሱም በተመሳሳይ መንገድ መለሰላት
"ጠላቶች እንድንሆን… አንቺን በደንብ ማወቅ እፈልጋለሁ።"አላት፡፡
"እኔም የመጣሁት ለዚህ ነው አቶ ፍሰሀ።"አለችው ፍርጥም ብላ፡፡
እሷን ትንሽ ጊዜ ወስዷ ሊያጠናት ሞከረ። "እንዴት ጠበቃ ለመሆን ፈለግሽ?"የተለመደ ግን ደግሞ ድንገተኛ ጥያቄ ጠየቃት፡፡
"የእናቴን ግድያ ለመመርመር ወንጀለኛውን ለፍርድ ለማቅረብ እንድችል.››
መልሱ በድንገት ወደ ከንፈሮቿ የመጣ ነው፣ ይህም መልሷ እንሱን ብቻ ሳይሆን አለምን እራሷን አስገርሟታል። እሷ ከዚህ በፊት የእናቷን ገዳይ መፈለግ ዋና ግቧ እንደሆነ ተናግራ አታውቅም።በዚህ የእናቷ ግድያ ወንጀል ላይ እሷ ራሷም በአያቷ ዘንድ ይፋዊ ተጠርጣሪ ሆና መቅረቧ ነገሩን በቁርጠኝነት እንድትይዘው ገፊ ምክንያት ሆኗታል፡፡ በመጨረሻ ሞት አፋፍ ላይ የምትገኝ አያቷ ለእናቷ ሞት ዋና ተጠያቂ እሷ እንደሆንች በግልፅ ቃል ደጋግማ ነግራታለች።አያቷ የተናገረችው ስህተት እንደሆነ የሚያረጋግጥ ሌላ ማስረጃ እስካላገኘች ድረስ ጥፋቱን እስከ ህይወቷ ድረስ ይዛ ለመኖር ትገደዳለች ። እና አሁን ከሻሸመኔ ከተማ ሃያሎቹ ጋር ተፋጣ የምትገኝት ዋና ምክንያት ራሷን ነፃ ለማውጣት ነው፡፡
አቶ ፍሰሀ "ባል የለሽም? ልጆችስ?"ሲል ሌላ ጥያቄ ጠየቃት፡፡
"አይ የለኝም።
" "ለምን?"
"አባ" አለ ጁኒየር በአባቱ እፍረት ማጣት አፍሮ ‹‹አለም ልተዝናና እንጂ በጥያቅህ እንድታጨናንቃት ይዣት አልመጣሁም››
" ጁኒየር ምንም ችግር የለውም። ይህ የተለመደ ጥያቄ ነው።"አለች አለም፡፡
" እሺ እንደዛ ካልሽ መልስሽ ምንድነው?"አቶ ፍሰሀ ጠየቃት፡፡
"ጊዜ ወይም ዝንባሌ የለኝም."
"በዚህ በእኛ አካባቢም ተመሳሳይ ብዙ ጊዜ እና በቂ ዝንባሌ የለንም."
ጁኒየር በጠወለገ እይታ አባቱን ተመለከተው።የተነገረው አሽሙር እሱን የሚመለከት እንደሆነ ያውቃል"አባዬ የከሸፉብኝን ትዳሮቼን እየጠቀሰ ነው።››በማለት አብራራላት፡፡
"ጋብቻዎች? ስንት ነበሩ?"አለም በጉጉት ጠየቀች
"ሶስት" በማለት ተናዘዘ።
"እና አንዳቸውም እኔን አያት የማድረግ ፍላጎቱም ሆነ ብቃት አልነበራቸውም››አቶ ፍሰሀ ዋና ቅሬታውን ተናገረ፡፡
በዚህ መካከል ከፎቁ ወደታች የሚወርድ የጫማ ኳኳታ ሰሙና በተመሳሳይ ሦስቱም ዞሩ። አንዲት ሴት በተከፈተው በር ላይ ቆማ ነበር። አለም የአቶ ፍሰሀ ሚስት እና የጁኒዬር እናት መሆኗን አወቀች። ከእግር ጥፍሯ እስከ ራስ ፀጉሯ ድረስ ምን እንደምትመስል አእምሮአዊ ምስል ቀርጾ ነበር። ወይዘሮዋ ግን የአለምን አእምሮአዊ ምስል ተቃራኒ ነበረች።
ጁኒዬር እናቴ ጀማይካዊት ነች ስላላት..የሆነች ፈርጣም ..ጠቆር ያለች.. ከንፈረ ትልልቅ…የፀጉሯ ድሬድ መቀመጫዋን የሚነካ አይነት አድርጋ ነበር የሳለቻት…እሷ ግን ቅንጥስጥስ ያለች ቀጭን…ቀይ ቆንጆ ግን ደግሞ ስልችት ያለው ፊት ያየዘች…ሀበሻ መሳይ
ሴት ነች፡፡ጁኒዬር ያንን አፍዛዣ መሳይ ውበቱን እና ለስላሳ ባህሪውን ከማን እንደወረሰው አሁን በግልፅ ገባት ፡፡
"ሃኒ ይህቺ አለም ጎበና ነች" አለ አቶ ፍሰሀ ።
የጁኒዬር እናት ባለቤቷን ችላ ብላ ፈካ ያለ ፊቷ አብርቶ ቀጥ ያለ ቀጭን ከንፈሯ ወደቀኝ በመጠምዘዝ ‹‹አለም ወደቤታችን እንኳን በሰላም መጣሽ…ሳራ እባላለው..የጁኒዬር እናት ነኝ
››አለችና ወንበር ስባ ተቀመጠች፡፡
አለም ከሴትዬዋ ንግግር የፍሰሀ ባለቤት ከመሆኗ በላይ የጁኒዬር እናት በመሆኗ ኩራት እንደሚሰማት ነው የተረዳችው፡፡
"አመሰግናለሁ።"ስትል መለሰች፡፡
ጁኒየር ከተቀመጠበት ተነሳና አንድ ብርጭቆ ነጭ ወይን ቀዳና ለእናቱ አቀበላት.. ። በሚያብረቀርቅ ፈገግታ‹‹አመሰግናለው የእኔ ልጅ››በማለት ተቀበለችው፡፡
እሱም ጎንበስ ብሎ እናቱን የለሰለሰ ስርጉድ ጉንጯን ሳመ። "ራስ ምታትሽ እንዴት ነው?"
"ሙሉ በሙሉ አልተወኝም፣ ነገር ግን እንቅልፍ ረድቶኛል። ስለጠየቅከኝ አመሰግናለሁ።"
አለም የሴትዬዋን እጇች ስታይ ተገረመች …እጇ ነጭ ሲሆኑ … በአውሎ ንፋስ እንደተመታ አበባ በቀላሉ ተሰባሪ ይመስላል።
ባሏን " መቼስ ስለከብቶችና ፈረሶች እያወራህ እያሰለቸሀት ነው አይደል?"አለችው፡፡
"በራሴ ቤት ውስጥ፣ ስለምንስ ባወራ አንቺን ምን ጨነቀሽ?" አቶ ፍሰሀ ቱግ አለ፡፡ ጁኒየር ንግግራቸውን ከዛ በላይ እንዳይጠነክርና አለም ፊት እንዳያሳፍሩን ፈጠን ብሎ ጣልቃ ገባ፡፡
"እማዬ ስለ እርባታ አይደለም እያወራን ያለነው ። አባዬ ከሚስቶቼ ወራሽ የሚሆን ልጅ ለመውለድ ባለመቻሌ እየወቀሰኝ ነበር።"ሲል አብራራላት፡፡
"ጊዜው ሲደርስ ከትክክለኛ ሴት ጋር ልጆች ትወልዳለህ››.አለችና ወደ አለም ዘወር ብላ ጠየቀች፡- “ወ.ሪት አለም በፍፁም አላገባሁም ስትይ ሰምቻለሁ ልበል ?” ብላ ጠየቀችው።
"ልክ ነው"
"እንግዳ ነገር ነው…ቢያንስ የወንድ ጓደኛ ሊኖርሽ ይገባ ነበር፡፡››
"አለም የወንድ ጓደኛ የለኝም አላለችም እኮ
››ጁኒየር አስተካከላት. "በቃ መራጭ ነች"ሲል አከለበት፡፡
"አዎ ከጋብቻ እና ቤተሰብ ከመመሥረት ይልቅ ሙያዬን መርጫለሁ።ለጊዜው፣ ለማንኛውም ነገር ጊዜ የለኝም። ግን እናቴ የሆነ ሙያ ባለቤት ለመሆን ፍላጎት እንዳላት ገልጻ ታውቃለች?"
"እሷን እስከማውቃት ድረስ እንደዛ አይነት ምኞት አልነበራትም" ሲል ጁኒየር መለሰ፣ አለም በፀፀት ስሜት "በጣም ቀድማ በልጅነቷ ነበር የወለደችኝ" አለች።
"ምናልባት ያለዕድሜ ጋብቻ ውስጥ መግባቷ እና ልጅ መውለዷ ወደ ሥራ እንዳትገባ አግዷት ይሆናል….ሰሎሜ የራሷን ምርጫ ነው ተግባራዊ ያደረገችው."ሲል መለሰላት፡፡
"የምታውቀውን ስለነገርከኝ አመሰግናለሁ.››
‹‹ አንድ ጊዜ እኔ እሷና ጀማል ለመዝናናት ወደወንዶ ገነት ሄደን ነበር፡፡በፍል ውሀ ስንታጠብና ስንዋኝ ከዋልን በኃላ በጣም ደክሞን ዛፍ ጥላ ስር ሳሩ ላይ ተዘርረን ሰማዩን አንጋጠን ስለ ምኞታችን ስናወራ እንደነበር ትዝ ይለኛል…ሁላችንም የዋና ልብስ ብቻ ነበር የለበስነው…እና እሷም በመሀላችን ተኝታ ነበር፡፡
❤44👍2
እኔ ፕሮፌሽናል እግርኳስ ተጫዋች መሆን ፈልግ ነበር…በወቅቱ ለእነሱም የነገርኳቸው ያንን ነው፡፡ ገመዶ ግን እንዴትም ብሎ እንዴት የሆነ ብር አግኝተ ሀብታም መሆን ነበር ምኞቱ ፤ ሀብታም መሆን እስከቻለ ድረስ ምንም አይነት ስራ ቢሰራ ግድ አይሰጠውም ነበር።እኔ ደግሞ የሀብታም ልጅ ስለነበርኩ እንደእሱ ላስብ አልችልም…. ሰሎሜ መሆን የምትፈልገው ግን ሚስት ብቻ ነበር።" ለአፍታ ቆም አለ እና እጆቹን ቁልቁል ተመለከተ።
‹‹እና አሁን ሳስበው ከእኔ በስተቀር ሁሉም ምኞታቸው የተሳካ ይመስለኛል…ሰሎሜ በአጭሩ ብትቀጭም ሚስት ሆና ልጅ መውለድ ችላለች…ገመዶም በዚህም ብሎ በዛ የሚፈልገውን ያህል ብር አግኝቷል ብዬ አስባለው ፡፡እኔ ብቻ ነኝ ያልተሳካልኝ፡፡››
አቶ ፍሰሀ ጆሮውን ወደውጭ እያቀና"ስለ ገመዶ ስትናገሩ ድምፁን የሰማሁ ይመስለኛል" አለ ፡ ፡
አለም ዘወር ስትል የተባለው ኩማንደር በበሩ በኩል ሲመጣ አየችው። የኩማንደሩ አስገራሚ መገለጥ ድንጋጤ ላይ ጥሏታል።
“ሄይ ገመዶ›› አለው ጁኒዬር፡፡
"ግባ።›› አቶ ፍሰሀ ወደ ክፍሉ ውስጥ እንዲዘልቅ በምልክት ጠራው። ሳራን ያላያት መስሎ ችላ አላት።አለምን እዛ ቤት በዛን ሰዓት በማየቱ እየተገረመ…..‹‹ሁላችሁንም ሳላም ብያለው…››በማለት ጃኬቱን አወለቀና ወንበር ስቦ ተቀመጠ፡፡
ጁኒዬር ተነስቶ ከፍሪጅ ውስጥ ዘወትር የሚጠጣውን አይነት ቢራ አምጥቶ ከፈተለትና ወደ ወንበሩ ተመልሶ ተቀመጠ፡፡
‹‹ዛሬ አለም እንግዳችን ነች››አለው አቶ ፍሰሀ፡፡
‹‹‹አየሁ እኮ …በየሄድኩበት እሷን ማግኘት መቻሌ እያስገረመኝ ነው››
ሁሉም ስለሚያወራው ነገር ግራ ተጋባ፡፡እሷም የዋዛ አልነበረችምና ወደእሱ በትኩረት እያየች"እዚህም የሆነ ነገር እንዳይነግሩኝ ልታስጠነቅቃቸው ነው ተከትለኸኝ የመጣኸው››አለችው፡፡
‹‹አረ..እንዴት እንደዛ ልትይ ቻልሽ..?ይሄ እኮ ቤቱ ነው››አቶ ፍሰሀ ነው ጣልቃ ገብቶ የተናገረው፡፡
፥‹‹ጥዋትም ..ዳኛውን እያወራው ሳለ ..ድንገት ቢሮውን ገፍትሮ ከፍቶ በመግባት ጣልቃ በመግባት ዝም አስብሏቸዋል….አሁንም እንደዛ ለማድረግ ፈልጎ እንደሆነ ብዬ ነው፡፡››
ኩማንደሩ ኮስተር እንዳለ"አንድ ሰው ቀጥተኛ ጥያቄ ሲጠይቀኝ የራሴን አስተያየት እሰጣለሁ…ጥዋት ያደረኩት እንደዛ ነው፡፡” ሲል መለሰላት፡፡
በዚህ ጊዜ ጭቅጭቃቸው ያላማረው አቶ ፍሰሀ
‹‹እናንተ ተጫወቱ..እኔ አቃቢ ፥ህጓን በግል ላናግራት እፈልጋለሁ። ከፈለግሽ ወይንሽን ይዘሽ ነይ" አላት ና ቀድሟት ከመቀመጫው ተነሳ፣እሷም ከተቀመጠችበት ያለምንም ማቅማማት ተነሳችና ተከተለችው ።እንዴት እንደ
ሆነ ሳታውቅ ከወንበሯ ተነስታ ወደ ኮሪደሩ ገባች። ሳሎኑን ለቆ ወደምድር ቤት ሲወርዱ ዙሪያውን ተመለከተች። ግድግዳዎቹ በቀይ የበግ ቆዳ ልጣፍ የተሸፍነ ነው… እና በፍሬም የተለበጡ በርካታ የፈረስ ፎቶግራፎች በተርታ ተደርድረዋል።
"ይሄንን ቤት ጁኒየር ገና ዳይፐር ያደርግበት በነበረበት ጊዜ እኔ ራሴ ነኝ ነድፌ የሠራሁት።››አላት፡፡
"አለም ሳይነግራት ቤቱን መገንባቱን ብቻ ሳይሆን ቤቱን በራሱ ፍላጎት እንዳስጌጠው ታውቅ ነበር። የሳራ ባህሪ የሚያንፀባርቅ ምንም ነገር በቤቱ የለም። ቤቱ በጣም አስቀያሚ ነበር፣ ነገር ግን በሚያስደነግጥ እና ይቅርታ በሌለው መጥፎ ጣዕም ውስጥ ስለነበር ልክ እንደ ፍሰሀ የራሱ የሆነ ማራኪ ውበት ነበረው። ይህ ቤት ከመሰራቱ በፊት እኔ እና ሳራ ጆ የምንኖረው በኪራይ ቤት ውስጥ ነበር። አለም ‹‹ወይዘሮ ሳራ የተዘናጋች እና ራሷን የረሳች አይነት ሴት ትመስላለች። ቤቱ ምኑም የእሷን አይመስልም፡፡››ስትል በውስጧ አሰበች፡፡
አቶ ፍሰሀ ግራጫ ቀለም ከተቀባው ግድግዳ ተጠግቶ ያለ በቀይ ቆዳ የተለበጠ ሶፋ ላይ ተቀመጠና….እሷም እድትቀመጥ ጋበዛት፡፡እንዳላት አደረገች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹እና አሁን ሳስበው ከእኔ በስተቀር ሁሉም ምኞታቸው የተሳካ ይመስለኛል…ሰሎሜ በአጭሩ ብትቀጭም ሚስት ሆና ልጅ መውለድ ችላለች…ገመዶም በዚህም ብሎ በዛ የሚፈልገውን ያህል ብር አግኝቷል ብዬ አስባለው ፡፡እኔ ብቻ ነኝ ያልተሳካልኝ፡፡››
አቶ ፍሰሀ ጆሮውን ወደውጭ እያቀና"ስለ ገመዶ ስትናገሩ ድምፁን የሰማሁ ይመስለኛል" አለ ፡ ፡
አለም ዘወር ስትል የተባለው ኩማንደር በበሩ በኩል ሲመጣ አየችው። የኩማንደሩ አስገራሚ መገለጥ ድንጋጤ ላይ ጥሏታል።
“ሄይ ገመዶ›› አለው ጁኒዬር፡፡
"ግባ።›› አቶ ፍሰሀ ወደ ክፍሉ ውስጥ እንዲዘልቅ በምልክት ጠራው። ሳራን ያላያት መስሎ ችላ አላት።አለምን እዛ ቤት በዛን ሰዓት በማየቱ እየተገረመ…..‹‹ሁላችሁንም ሳላም ብያለው…››በማለት ጃኬቱን አወለቀና ወንበር ስቦ ተቀመጠ፡፡
ጁኒዬር ተነስቶ ከፍሪጅ ውስጥ ዘወትር የሚጠጣውን አይነት ቢራ አምጥቶ ከፈተለትና ወደ ወንበሩ ተመልሶ ተቀመጠ፡፡
‹‹ዛሬ አለም እንግዳችን ነች››አለው አቶ ፍሰሀ፡፡
‹‹‹አየሁ እኮ …በየሄድኩበት እሷን ማግኘት መቻሌ እያስገረመኝ ነው››
ሁሉም ስለሚያወራው ነገር ግራ ተጋባ፡፡እሷም የዋዛ አልነበረችምና ወደእሱ በትኩረት እያየች"እዚህም የሆነ ነገር እንዳይነግሩኝ ልታስጠነቅቃቸው ነው ተከትለኸኝ የመጣኸው››አለችው፡፡
‹‹አረ..እንዴት እንደዛ ልትይ ቻልሽ..?ይሄ እኮ ቤቱ ነው››አቶ ፍሰሀ ነው ጣልቃ ገብቶ የተናገረው፡፡
፥‹‹ጥዋትም ..ዳኛውን እያወራው ሳለ ..ድንገት ቢሮውን ገፍትሮ ከፍቶ በመግባት ጣልቃ በመግባት ዝም አስብሏቸዋል….አሁንም እንደዛ ለማድረግ ፈልጎ እንደሆነ ብዬ ነው፡፡››
ኩማንደሩ ኮስተር እንዳለ"አንድ ሰው ቀጥተኛ ጥያቄ ሲጠይቀኝ የራሴን አስተያየት እሰጣለሁ…ጥዋት ያደረኩት እንደዛ ነው፡፡” ሲል መለሰላት፡፡
በዚህ ጊዜ ጭቅጭቃቸው ያላማረው አቶ ፍሰሀ
‹‹እናንተ ተጫወቱ..እኔ አቃቢ ፥ህጓን በግል ላናግራት እፈልጋለሁ። ከፈለግሽ ወይንሽን ይዘሽ ነይ" አላት ና ቀድሟት ከመቀመጫው ተነሳ፣እሷም ከተቀመጠችበት ያለምንም ማቅማማት ተነሳችና ተከተለችው ።እንዴት እንደ
ሆነ ሳታውቅ ከወንበሯ ተነስታ ወደ ኮሪደሩ ገባች። ሳሎኑን ለቆ ወደምድር ቤት ሲወርዱ ዙሪያውን ተመለከተች። ግድግዳዎቹ በቀይ የበግ ቆዳ ልጣፍ የተሸፍነ ነው… እና በፍሬም የተለበጡ በርካታ የፈረስ ፎቶግራፎች በተርታ ተደርድረዋል።
"ይሄንን ቤት ጁኒየር ገና ዳይፐር ያደርግበት በነበረበት ጊዜ እኔ ራሴ ነኝ ነድፌ የሠራሁት።››አላት፡፡
"አለም ሳይነግራት ቤቱን መገንባቱን ብቻ ሳይሆን ቤቱን በራሱ ፍላጎት እንዳስጌጠው ታውቅ ነበር። የሳራ ባህሪ የሚያንፀባርቅ ምንም ነገር በቤቱ የለም። ቤቱ በጣም አስቀያሚ ነበር፣ ነገር ግን በሚያስደነግጥ እና ይቅርታ በሌለው መጥፎ ጣዕም ውስጥ ስለነበር ልክ እንደ ፍሰሀ የራሱ የሆነ ማራኪ ውበት ነበረው። ይህ ቤት ከመሰራቱ በፊት እኔ እና ሳራ ጆ የምንኖረው በኪራይ ቤት ውስጥ ነበር። አለም ‹‹ወይዘሮ ሳራ የተዘናጋች እና ራሷን የረሳች አይነት ሴት ትመስላለች። ቤቱ ምኑም የእሷን አይመስልም፡፡››ስትል በውስጧ አሰበች፡፡
አቶ ፍሰሀ ግራጫ ቀለም ከተቀባው ግድግዳ ተጠግቶ ያለ በቀይ ቆዳ የተለበጠ ሶፋ ላይ ተቀመጠና….እሷም እድትቀመጥ ጋበዛት፡፡እንዳላት አደረገች፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤24👍24
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ከዛ ጉሮሮውን አሟሸና መናገር ጀመረ"ከእድሜሽ በላይ ለማሸነፍ ስጥር ነው የኖርኩት…እናም ቡዙ ነገር አግኝቼ .. ብዙ ነገር አጥቻለሁ፣ ወጣቷ ሴት…ኪሳራ አያስደነግጠኝም። ሀብታም መሆን የበለጠ አስደሳች ነገር ነው፣ ግን ኪሳራም የበለጠ አስደሳች ነው። እራስን የሚያንፁና የሚገነቡ ጥቅሞች አሉት። ››
‹‹ከከተማዋም አልፎ በሀገሪቱም የተሳካልህ የቢዝነስ ሰው መሆንህን አውቃለው፡፡ገንዘብ ስላለህም የፈለከውን ነገር በፈለከው ሰዓት ማድረግ እንደምትችል እንደምታምንም አውቃለው፡፡››አለችው በልበሙሉነት፡፡
"ታዲያ ካወቅሽ ይህን አስቂኝ ምርመራ ለምን አትተይውም?"ሲል ቀጥታ ወደሚፈልገው ርዕስ ገባ፡፡
"ይህ መቼም የሚሆን አይመስለኝም ..አላደርገውም››
"እናትሽን የገደልኩት እኔ እንደሆንኩ እንዴት ታስቢያለሽ? እሷ ከጁኒየር ምርጥ ጓደኞች መካከል አንዷ ነበረች:: በየእለቱ ከዚህ ቤት ትወጣና ትገባ ነበር::እርግጥ ካገባች በኋላ ብዙም አትመጣም ነበር… እናትሽን ለመጉዳት ጣቴን አንስቼ አላውቅም።››
አለም እሱን ማመን ፈለገች። በወንጀል ጉዳይ ተጠርጣሪ ቢሆንም እሷ ግን በጣም ታደንቀው ነበር። በውይይታቸው ከተገነዘበችው እና ለምርመራዋ ስትል ከሰበሰበችው መራጃ እንደተረዳችው ከምንም ነገር ተነስቶ ኢምፓየር መገንባት ችሏል።በማህበረሰቡ ዘንድ በጣም ተወዳጅ ነበር. አሳማኝ ባህሪ ነበረው። ነገር ግን በቀለማት ያሸበረቀ ስብዕናው ከጀርባ ሚሰራቸውን ቆሻሻ ድርጊቷች በቀላሉ እንዳይገለፁ ምክንያት እንደሆኑ በደንብ ታውቃለች።ቢሆንም ግን ለፍሰሀ ያላት አድናቆት እንደፍላጎቷ ሙሉና ጠንካራ አልነበረም..፡፡
ደገመችና ‹‹ምንም ቢሆን ምንም ምርመራውን ማቋረጥ አልችልም" አለች ።
‹‹ለምን ?››
" ብፈልግ እንኳን ዋና አቃቢ ህጉን በስንት መከራ ካሳመንኩት በኃላ ወደኃላ እንድመለስ መጠየቅ ያሳፍራል ፡፡"
"ስሚ" አለና አይኖቾን በትኩረት እያየ " ስህተት እንደሰራሽ ንገሪው፣ እናም ነገ በዚህ ሰአት እዚህ የመጣሽበትን ጉዳይ እንኳን እንደማያስታውስ ዋስትና እሰጥሻለሁ..ስራውንም ለቀሽ ወደአዲስአበባ መመለስና ቆንጆ የጥብቅና ቢሮ ማቋቋም ትችያለሽ….እናትሽ የልጄ የልብ ጓደኛ ነች…አንቺን ለማቋቋም የሆነ ነገር ማድረግ ለእኔ ያን ያህል የሚከብድ ጉዳይ አይደለም ።"
" አላደርገውም "
"እሺ፣ እንግዲያውስ ዋና አቃቢ ህጉን ለእኔ ተይልኝ..እኔ አናግረዋለው።"
"አቶ ፍሰሀ… ››ጮክ ብላ ተናገረች "የኔ ሀሳብ አልተረዳህልኝም"ትኩረቱን እንዳገኘች እርግጠኛ ስትሆን "ልጅህ በምርጫ ያለውን ተሳትፎ የሚጎዳ ምንም ነገር ለማድረግ እቅድ የለኝም…ያ እንዳይሆን አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንደማደርግና እያንዳንዱን እንቅስቃሴዬንና ምርመራዬን በከፍተኛ ሚስጥር እንደማከናውን ቃል እገባለው…ማድረግ የምችለው ያንን ብቻ ነው፡፡››
"የአንድ ሙሉ ከተማ የወደፊት ዕጣ ፈንታ አደጋ ላይ ቢሆንም ሀሳብሽን አትቀይሪም ማለት ነው?"
"ከተራቡ ህፃናት ዳቦ እየወሰድኩ ነው የሚመስልህ…?ነው ወይስ ያንተ ልጅ ይህቺን ከተማ ወክሎ የተወካዬች ምክር ቤት ከገባ በኩልፎ ወንዝ ወተት እንደሚንዠቀዘቅ እና ህዝቡ በቁንጣን እንደሚሰቃይ ነው የምታስበው?"
" ተይ እንጂ ..እኔ እንደዛ አላልኩም "
" እንግዲያው አቋሜን በግልፅ አሳውቂያለው..እኔ ሁላችሁንም በግል ለማጥቃትና ለማውደም ምንም እቅድ የለኝም…ግን ደግሞ የእናቴን ገዳይ ለፍርድ ለማቅረብ ህይወቴንም የሚያስከፍለኝ ቢሆን ግድ የለኝም..እስትንፋሴ እስካለች ድረስ ወደፊት እቀጥላለው››
‹‹በቃ የመጨረሻ ውሳኔሽ ይሄ ነው?"
‹‹አዎ..እኔን ማስቆሚያ ብቸኛው መንገድ እኔንም እንደእናቴ ማስወገድ ነው….በዛ ጉዳይ ላይ ልታስብበት ትችላላችሁ፡፡››
‹‹ንግግርሽ በጣም….››አቶ ፍሰሀ ንግግሩን አቋረጠ..እንደዛ ያደረገው ልጁ ጂኒዬር በራፉን ከፍቶ ስለገባ ነው፡፡
ጁኒየር በሩን በድንገት ከፍቶ አንገቱን ወደ ውስጥ አሰገገና"ሄይ, በሰላም ነው ..በጣም መሸ እኮ…እራት ሊቀርብ ነው" ፡፡
"በጣም ጥሩ ….ውይይታችን ጨርሰናል…..ግን እራቱ ይቅርብኝ ….ቀጥታ ወደቤቴ ነው መሄድ የምፈልገው››አለች አለም።
አቶ ፍሰሀ ንዴቱን መቆጣጠር አቃተው "እዚህ በቁም ነገር እየተነጋገርን ነበር። ዳግመኛ በግል ቢሮዬ ውስጥ ከሰው ጋር እያለው አንዳታቋርጠኝ፣ ።››
ጁኒየር "ንግግራችሁ በጣም ግላዊ ወይም በጣም ከባድ እንደሆነ አላውቅም ነበር።"ሲል ለአባቱ ቅሬታ ምላሽ ሰጠ፡፡
"አቶ ፍሰሀ.. እባክህ, ምንም አይደለም…በበቂ መጠን ተጋግረናል እኮ..የቀረም ነገር ካለ ሁለተችንም እዚሁ ከተማ ውስጥ ነን..ደጋግመን መገናኘታችን አይቀርም በእውነቱን ለመናገር፣ ጁኒየር ስላቋረጠን ደስተኛ ነኝ። ምን ያህል እንደመሸ አሁን ነው ያስተዋልኩት… አሁን መሄድ አለብኝ።"
ሁሉም ተያይዘው ወደሳሎን ተመለሱ፡፡ሳሎኑ ባዶ ነበር፡፡ገመዶም ሆነ ሳራ አልነበሩም፡፡
‹‹ለራት ብትቆይ ግን ደስ ይለኛል››አቶ ፍሰሀ ናቸው ተናጋሪው
‹‹አይ ይቅርብኝ..ደህና እደሩ››
ጁኒየር ኮቷን ከያዘላት በኋላ መኪናዋ ድረስ ሸኛት ..ወደ እሱ ዘወር አለችና ።"ጁኒየር አመሰግናለው …ደህና እደር።"አለችው
" እጇን ያዘና ጎንበስ ብሎ ሳመው… ከዛ መዳፏን ወደ ላይ አዙሮ ሳመው። "የምታገኛቸው ሴቶች ሁሉ እንደዚህ ታሽኮረምማለህ?"
የማይገባ ፈገግታ ፈገግ አለላት ፡፡
"ለፍቅር በቀላሉ ተጋላጭ ነህ እንዴ?"ሌላ ጥያቄ አስከተለች፡፡ "እንደዛ ነኝ እንዴ..?አይ አይደለሁም."ፈገግታው እየሰፋ ሄዶ ፡፡
‹‹ለማንኛም መልካም ምሽት››አለችና መኪና ውስጥ ገብታ አካባቢውን ለቃ ተፈተለከች ጁኒዬር ወደቤት ተመለሰና ቀጥታ ወደእናቱ መኝታ ክፈል አመራ እና በስሱ አንኳኳ
‹‹እማዬ ፣ ልግባ?››
" ውዴ እባክህ ግባ" ሳራ ፈቀደችለት… በልጇ ጉብኝት በጣም እንደተደሰተች ግልጽ ነው። ርካሽ የንባብ መነፅሯን አውልቃ እያነበበች የነበረውን መፅሃፉ ከጎኗ አስቀመጠች፡፡
‹‹አትቀመጥም››
‹‹አይ ይሁን›› አለና አልጋው ጎን በመቆም፡፡
"መጽሐፉ እንዴት ነው?" ሲል ጠየቃት፡፡መፅሀፉን ገዝቶ ያመጣላት እሱ ነበር፡፡
"በጣም አስደሳች ነው።››ስትል በአጭሩ መለሰችለት፡፡ "ጥሩ፣ ስለተደሰትሽበት ደስ ብሎኛል"
ሳራ እናቱ እንደመኆኗ መጠን በውስጡ የሚገላበጠውን ጭንቀት ተረዳችና። "ምንድነው ችግሩ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
"ምንም።"
"አንድ የተሳሳተ ነገር ሲኖር ማወቅ እችላለሁ."
"ከተለመደው የተለየ ነገር የለም ከአሌክስ..ማለቴ ከአለም ጋር የነበራቸውን ውይይት በማቋረጤ አባቴን አበሳጭቼዋለው››
"አባትህ የጋራችን በሆነው መኖሪያ ቤታችን ውስጥ ሲኖር ራሱን እንዴት መምራት እንዳለበት እስካሁን አልተማረም። በቤታችን የጋራ እንግዳችን ሆና የመጣችን ሴት ለግል ውይይት ብሎ ክፍል ውስጥ በማስገባት ማዋራት ጨዋነት የጎደለው ተግባር ስለሆነ አንተም ፣ ውይይቱን በማቋረጥ ባለጌ የመሆን መብት አለህ።››አለችው
‹‹እማዬ…››
"ለማንኛውም በግል ምን እየተወያዩ ነበር?"
"ስለ እናቷ ሞት ይመስለኛል….ምንም የሚያስጨንቅ ነገር የለም."
"እርግጠኛ ነህ? ዛሬ ማታ ሁሉም ሰው በጣም የተጨናነቀ ስሜት ላይ እንዳለ መረዳት ችያለው።"
" ችግርም ካለ አባዬ ሁል ጊዜ እንደሚያደርገው ይቆጣጠረዋል። በእርግጠኝነት ምንም የሚያስጨንቅ ነገር አይኖርም።››
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
ከዛ ጉሮሮውን አሟሸና መናገር ጀመረ"ከእድሜሽ በላይ ለማሸነፍ ስጥር ነው የኖርኩት…እናም ቡዙ ነገር አግኝቼ .. ብዙ ነገር አጥቻለሁ፣ ወጣቷ ሴት…ኪሳራ አያስደነግጠኝም። ሀብታም መሆን የበለጠ አስደሳች ነገር ነው፣ ግን ኪሳራም የበለጠ አስደሳች ነው። እራስን የሚያንፁና የሚገነቡ ጥቅሞች አሉት። ››
‹‹ከከተማዋም አልፎ በሀገሪቱም የተሳካልህ የቢዝነስ ሰው መሆንህን አውቃለው፡፡ገንዘብ ስላለህም የፈለከውን ነገር በፈለከው ሰዓት ማድረግ እንደምትችል እንደምታምንም አውቃለው፡፡››አለችው በልበሙሉነት፡፡
"ታዲያ ካወቅሽ ይህን አስቂኝ ምርመራ ለምን አትተይውም?"ሲል ቀጥታ ወደሚፈልገው ርዕስ ገባ፡፡
"ይህ መቼም የሚሆን አይመስለኝም ..አላደርገውም››
"እናትሽን የገደልኩት እኔ እንደሆንኩ እንዴት ታስቢያለሽ? እሷ ከጁኒየር ምርጥ ጓደኞች መካከል አንዷ ነበረች:: በየእለቱ ከዚህ ቤት ትወጣና ትገባ ነበር::እርግጥ ካገባች በኋላ ብዙም አትመጣም ነበር… እናትሽን ለመጉዳት ጣቴን አንስቼ አላውቅም።››
አለም እሱን ማመን ፈለገች። በወንጀል ጉዳይ ተጠርጣሪ ቢሆንም እሷ ግን በጣም ታደንቀው ነበር። በውይይታቸው ከተገነዘበችው እና ለምርመራዋ ስትል ከሰበሰበችው መራጃ እንደተረዳችው ከምንም ነገር ተነስቶ ኢምፓየር መገንባት ችሏል።በማህበረሰቡ ዘንድ በጣም ተወዳጅ ነበር. አሳማኝ ባህሪ ነበረው። ነገር ግን በቀለማት ያሸበረቀ ስብዕናው ከጀርባ ሚሰራቸውን ቆሻሻ ድርጊቷች በቀላሉ እንዳይገለፁ ምክንያት እንደሆኑ በደንብ ታውቃለች።ቢሆንም ግን ለፍሰሀ ያላት አድናቆት እንደፍላጎቷ ሙሉና ጠንካራ አልነበረም..፡፡
ደገመችና ‹‹ምንም ቢሆን ምንም ምርመራውን ማቋረጥ አልችልም" አለች ።
‹‹ለምን ?››
" ብፈልግ እንኳን ዋና አቃቢ ህጉን በስንት መከራ ካሳመንኩት በኃላ ወደኃላ እንድመለስ መጠየቅ ያሳፍራል ፡፡"
"ስሚ" አለና አይኖቾን በትኩረት እያየ " ስህተት እንደሰራሽ ንገሪው፣ እናም ነገ በዚህ ሰአት እዚህ የመጣሽበትን ጉዳይ እንኳን እንደማያስታውስ ዋስትና እሰጥሻለሁ..ስራውንም ለቀሽ ወደአዲስአበባ መመለስና ቆንጆ የጥብቅና ቢሮ ማቋቋም ትችያለሽ….እናትሽ የልጄ የልብ ጓደኛ ነች…አንቺን ለማቋቋም የሆነ ነገር ማድረግ ለእኔ ያን ያህል የሚከብድ ጉዳይ አይደለም ።"
" አላደርገውም "
"እሺ፣ እንግዲያውስ ዋና አቃቢ ህጉን ለእኔ ተይልኝ..እኔ አናግረዋለው።"
"አቶ ፍሰሀ… ››ጮክ ብላ ተናገረች "የኔ ሀሳብ አልተረዳህልኝም"ትኩረቱን እንዳገኘች እርግጠኛ ስትሆን "ልጅህ በምርጫ ያለውን ተሳትፎ የሚጎዳ ምንም ነገር ለማድረግ እቅድ የለኝም…ያ እንዳይሆን አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንደማደርግና እያንዳንዱን እንቅስቃሴዬንና ምርመራዬን በከፍተኛ ሚስጥር እንደማከናውን ቃል እገባለው…ማድረግ የምችለው ያንን ብቻ ነው፡፡››
"የአንድ ሙሉ ከተማ የወደፊት ዕጣ ፈንታ አደጋ ላይ ቢሆንም ሀሳብሽን አትቀይሪም ማለት ነው?"
"ከተራቡ ህፃናት ዳቦ እየወሰድኩ ነው የሚመስልህ…?ነው ወይስ ያንተ ልጅ ይህቺን ከተማ ወክሎ የተወካዬች ምክር ቤት ከገባ በኩልፎ ወንዝ ወተት እንደሚንዠቀዘቅ እና ህዝቡ በቁንጣን እንደሚሰቃይ ነው የምታስበው?"
" ተይ እንጂ ..እኔ እንደዛ አላልኩም "
" እንግዲያው አቋሜን በግልፅ አሳውቂያለው..እኔ ሁላችሁንም በግል ለማጥቃትና ለማውደም ምንም እቅድ የለኝም…ግን ደግሞ የእናቴን ገዳይ ለፍርድ ለማቅረብ ህይወቴንም የሚያስከፍለኝ ቢሆን ግድ የለኝም..እስትንፋሴ እስካለች ድረስ ወደፊት እቀጥላለው››
‹‹በቃ የመጨረሻ ውሳኔሽ ይሄ ነው?"
‹‹አዎ..እኔን ማስቆሚያ ብቸኛው መንገድ እኔንም እንደእናቴ ማስወገድ ነው….በዛ ጉዳይ ላይ ልታስብበት ትችላላችሁ፡፡››
‹‹ንግግርሽ በጣም….››አቶ ፍሰሀ ንግግሩን አቋረጠ..እንደዛ ያደረገው ልጁ ጂኒዬር በራፉን ከፍቶ ስለገባ ነው፡፡
ጁኒየር በሩን በድንገት ከፍቶ አንገቱን ወደ ውስጥ አሰገገና"ሄይ, በሰላም ነው ..በጣም መሸ እኮ…እራት ሊቀርብ ነው" ፡፡
"በጣም ጥሩ ….ውይይታችን ጨርሰናል…..ግን እራቱ ይቅርብኝ ….ቀጥታ ወደቤቴ ነው መሄድ የምፈልገው››አለች አለም።
አቶ ፍሰሀ ንዴቱን መቆጣጠር አቃተው "እዚህ በቁም ነገር እየተነጋገርን ነበር። ዳግመኛ በግል ቢሮዬ ውስጥ ከሰው ጋር እያለው አንዳታቋርጠኝ፣ ።››
ጁኒየር "ንግግራችሁ በጣም ግላዊ ወይም በጣም ከባድ እንደሆነ አላውቅም ነበር።"ሲል ለአባቱ ቅሬታ ምላሽ ሰጠ፡፡
"አቶ ፍሰሀ.. እባክህ, ምንም አይደለም…በበቂ መጠን ተጋግረናል እኮ..የቀረም ነገር ካለ ሁለተችንም እዚሁ ከተማ ውስጥ ነን..ደጋግመን መገናኘታችን አይቀርም በእውነቱን ለመናገር፣ ጁኒየር ስላቋረጠን ደስተኛ ነኝ። ምን ያህል እንደመሸ አሁን ነው ያስተዋልኩት… አሁን መሄድ አለብኝ።"
ሁሉም ተያይዘው ወደሳሎን ተመለሱ፡፡ሳሎኑ ባዶ ነበር፡፡ገመዶም ሆነ ሳራ አልነበሩም፡፡
‹‹ለራት ብትቆይ ግን ደስ ይለኛል››አቶ ፍሰሀ ናቸው ተናጋሪው
‹‹አይ ይቅርብኝ..ደህና እደሩ››
ጁኒየር ኮቷን ከያዘላት በኋላ መኪናዋ ድረስ ሸኛት ..ወደ እሱ ዘወር አለችና ።"ጁኒየር አመሰግናለው …ደህና እደር።"አለችው
" እጇን ያዘና ጎንበስ ብሎ ሳመው… ከዛ መዳፏን ወደ ላይ አዙሮ ሳመው። "የምታገኛቸው ሴቶች ሁሉ እንደዚህ ታሽኮረምማለህ?"
የማይገባ ፈገግታ ፈገግ አለላት ፡፡
"ለፍቅር በቀላሉ ተጋላጭ ነህ እንዴ?"ሌላ ጥያቄ አስከተለች፡፡ "እንደዛ ነኝ እንዴ..?አይ አይደለሁም."ፈገግታው እየሰፋ ሄዶ ፡፡
‹‹ለማንኛም መልካም ምሽት››አለችና መኪና ውስጥ ገብታ አካባቢውን ለቃ ተፈተለከች ጁኒዬር ወደቤት ተመለሰና ቀጥታ ወደእናቱ መኝታ ክፈል አመራ እና በስሱ አንኳኳ
‹‹እማዬ ፣ ልግባ?››
" ውዴ እባክህ ግባ" ሳራ ፈቀደችለት… በልጇ ጉብኝት በጣም እንደተደሰተች ግልጽ ነው። ርካሽ የንባብ መነፅሯን አውልቃ እያነበበች የነበረውን መፅሃፉ ከጎኗ አስቀመጠች፡፡
‹‹አትቀመጥም››
‹‹አይ ይሁን›› አለና አልጋው ጎን በመቆም፡፡
"መጽሐፉ እንዴት ነው?" ሲል ጠየቃት፡፡መፅሀፉን ገዝቶ ያመጣላት እሱ ነበር፡፡
"በጣም አስደሳች ነው።››ስትል በአጭሩ መለሰችለት፡፡ "ጥሩ፣ ስለተደሰትሽበት ደስ ብሎኛል"
ሳራ እናቱ እንደመኆኗ መጠን በውስጡ የሚገላበጠውን ጭንቀት ተረዳችና። "ምንድነው ችግሩ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
"ምንም።"
"አንድ የተሳሳተ ነገር ሲኖር ማወቅ እችላለሁ."
"ከተለመደው የተለየ ነገር የለም ከአሌክስ..ማለቴ ከአለም ጋር የነበራቸውን ውይይት በማቋረጤ አባቴን አበሳጭቼዋለው››
"አባትህ የጋራችን በሆነው መኖሪያ ቤታችን ውስጥ ሲኖር ራሱን እንዴት መምራት እንዳለበት እስካሁን አልተማረም። በቤታችን የጋራ እንግዳችን ሆና የመጣችን ሴት ለግል ውይይት ብሎ ክፍል ውስጥ በማስገባት ማዋራት ጨዋነት የጎደለው ተግባር ስለሆነ አንተም ፣ ውይይቱን በማቋረጥ ባለጌ የመሆን መብት አለህ።››አለችው
‹‹እማዬ…››
"ለማንኛውም በግል ምን እየተወያዩ ነበር?"
"ስለ እናቷ ሞት ይመስለኛል….ምንም የሚያስጨንቅ ነገር የለም."
"እርግጠኛ ነህ? ዛሬ ማታ ሁሉም ሰው በጣም የተጨናነቀ ስሜት ላይ እንዳለ መረዳት ችያለው።"
" ችግርም ካለ አባዬ ሁል ጊዜ እንደሚያደርገው ይቆጣጠረዋል። በእርግጠኝነት ምንም የሚያስጨንቅ ነገር አይኖርም።››
❤38👍4
ስለ አለም ምርመራ ለእናቱ የመንገር ፍላጎት አልነበረውም። ሳራ በህይወቷ ውስጥ የሚረብሻት ነገር እንዲኖር አትፈልግም..ወዲያው ነው የምትሰባበረው።ባለቤቷ ፍሰሀ ከእሷ ጋር ስለ ንግድ ሥራ ተወያይቶ አያውቅም ፣ በተለይም መጥፎ በሚሆንበት ጊዜ እሷ ጆሮ እንዳይደርስ በጣም ይጠነቀቃል። እሷም በዛው ልክ ስለኢንተርፕራይዙ ስኬትም ሆነ ውድቀት ለመስማት ምንም አይነት ጉጉት አሳይታ አታውቅም፡፡
እሷ በቤቱ ውስጥ ልክ እንደ ውብ አሻንጉሊት ነበረች፣ በጸዳ ክፍል ውስጥ እንደታሸገች ምትኖር ነበርች፡፡፣ ለብርሃንም ሆነ ለሌላ ጎጂ ነገር እራሷን በጭራሽ አታጋለጥም።ጁኒየር እናቱን ይወዳታል፣ ግን በደንብ እንዳልተንከባከባት ያውቃል፡፡
"ስለ እሷ ምን አሰብሽ?"ሲል ጠየቃት፡፡
"የሰሎሜን ሴት ልጅ ማለትህ ነው? ምንም እንኳን የእንደዚህ አይነት ደማቅ ሴት አድናቂ ባልሆንም በአካል በጣም ማራኪ ነች፣በእርግጥም እሷ በጣም ኃይለኛ ነች አይደል? ከእናቷ የበለጠ ቁም ነገር ያላት ትመስለኛለች… ሰሎሜ ትንሽ ደደብ ነገር ነበረች፣ እንደማስታውሰው ሁል ጊዜ ትስቅ ነበር።" ቆም ብላ ጭንቅላቷን ወደ አንድ ጎን ነቀነቀች፣ የሩቅ ሳቋን የምትሰማ ያህል ምታዳምጥ ትመስላለች። "ያህቺኛዋን ልጅ ግን ስትስቅ እንዳየኋት አላስታውስም።"
‹‹አዎ…በተወሰነ መልኩ ትክክል ነሽ››አላት
" ምስኪን የእኔ ልጅ እሷ ስትሞት በጣም ተጎድተህ እንደነበረ አውቃለሁ፣ የምትወደውን ሰው ማጣት ምን እንደሚመስል አውቃለሁ። ያ ባንተ ህይወት ውስጥ የተከሰተ ከባድ መከራ ነበር።››
‹‹አዎ እማዬ….በመሞቷ በጣም አዝኛለሁ››
በጣም ለስላሳ የነበረው ድምጿ በድንገት ተለወጠ። "ጁኒየር፣ በተለይ በሌሎች ሰዎች ፊት አባትህ እንዲያሳፍርህ መፍቀድ የለብህም።››ስትል ወደቀደመ ውይይታቸው መለሰችው፡፡
" ምንም ማለት አይደለም አባዬን ታውቂዋለሽ… ለክፋት ብሎ ሳይሆን ልማድ ሆኖበት ነው እንደዛ የተናገርኝ››
"እንዲህ እንድታስብ ነው የሚፈልገው። ሁል ጊዜ ለእሱ የብልግና ድርጊት ምክንያት እንድትፈልግለት ይፈልጋል። ፍሰሀ የሚያውቀው አንድ ድምፅ ብቻ ነው። ቁጣና ስድብ፡፡ልጄ እሱ እንደ እኛ ለስላሳ እና ገር መሆን አያውቅም። ልክ እንደ ገመዶ በሚገባው መንገድ ከእሱ ጋር መነጋገር አለብህ። ፍሰሀ አንተ ላይ በሚጮኸው መንገድ ገመዶን ሲያናግረው አይተህ ታውቃህ..?በፍፁም እሱን ደፍሮ አይዘረጥጠውም። ››
"አባዬ ገመዶ ምንም አይነት ስህተት እንደማይሰራ ያስባል። መላ ካምፓኒውን ከእኔ ይልቅ ኩማንደሩ ቢያስተዳድርለት ይመርጣል።አንድም ቀን በእኔ ስራ እርካታ ተሰምቶት አያውቅም››ብሎ በምሬት የተጠራቀመ ቅሬታውን ተናገረ፡፡
"ያ ፈፅሞ እውነት አይደለም!" ሳራ በሳምንታት ውስጥ ከነበራት የበለጠ ጠንካራ መንፈስ በማሳየት ተቃወመች። "ፍሰሀ በአንተ በጣም ይኮራብሃል። እንዴት ማሳየት እንዳለበት ግን አያውቅም። እሱ በጣም ከባድ ሰው ነው። በዙሪያው ያሉ ነገሮችን ሁሉ ለመቋጣጠር እንዲችል ሁሌ ጠንክራ እና ኮስታራ ሆኖ መታየት እዳለበት ነው የሚያምነው ። አንተም በእሱ መጠን ጠንካራ እንድትሆንለት ይፈልጋል።"
ጁኒየር ፈገግ አለ፣ "እሺ እናቴ፣ አሁን ወጣ ብዬ ራሴን ዘና ላድርግ…ነገ ጠዋት እየተንገዳገድኩ እመጣለሁ።››
ሳቀች ። በእሱ ፍቅር ውስጥ የተደበቀ ጥንካሬ እና ቀልድ ሁልጊዜ ያስደስታት ነበር። "ተስፋ አደርጋለሁ፣ ነገር ግን ጥንካሬ ፍሰሀ በአንተ ውስጥ ማየት የሚፈልገው መንፈስ ነው።››
ጁኒየር ‹‹ደህና እደሪ እማዬ››አለና ጎንበስ ብሎ ጉንጯን ሳመ፡፡
‹‹ቀስ ብለህ ንዳ..ደግሞ ብዙ እንዳትጠጣ ››የተለመደ የእናትነት ምክሯን ለገሰችው፡፡
እናቱን መኝታ ቤት ለቆ ወደሳሎን ሲመለስ አባቱን ምቹ ወንበሩ ላይ ቁጭ ብሎ ቢራውን እየተጎነጨ በሀሳብ ተውጦ አገኘው፡፡
"ያቺን ልጅ ወደዚህ ቤት ለማምጣት በአንተ ላይ መደገፍ እንደምችል አውቅ ነበር. እንደ አስብኩት ተሳክቷልሀል. የነበራትን ቁርጠኝነትና ጉጉት የሚሸረሽር ነገሮችን ማድረግ ችለናል.. ብልህ ከሆነች ብዙ ጉዳት ከመድረሱ በፊት ይህንን የጀመረችውን ነገር ታቆማለች..ደግሞ ብልህ ነችም ብዬ አስባለው፡፡››አለው
" ባታደርገውስ?"ጁኒዬር ጥርጣሬውን አነሳ፡፡
"እሷ ካላደረገች እኛም ያንን ድልድይ እናቋርጣለን" አለ አቶ ፍሰሀ።ከተቀመጠበት በመነሳት ፈገግ አለ እና በፍቅር ስሜት የጁኒየርን ጉንጩ ነካ በማድረግ "ደህና እደር ልጄ"ብሎ ወደመኝታ ቤቱ ተጓዘ፡፡
ጁኒየር አባቱ ወደመኝታው ሲሄድ ቆሞ ተመለከተው። በጣም ጥሩ ስሜት ስለተሰማው፣ በቆመበት ፈገግ አለ። አባቱ በእርሱ ቅር እንዳልተሰኘበት ገባው። ሴቶችን በማስተናገድ ረገድ የነበረው ልምድ በጣም የተዋጣለት ነበር። አለም የተረገመች ማራኪ ሴት ነበረች። አባቱ ባይነግረውም ኖሮ ለማንኛውም ያማልላት ነበር። ኮሪደሩን አቆርጦ ወደ ከፊት ለፊት በር ሲወጣ በመስታወት ውስጥ ለተመለከተው የገዛ ቆንጆ ቁመናው ሰላምታ ሰጠ።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
እሷ በቤቱ ውስጥ ልክ እንደ ውብ አሻንጉሊት ነበረች፣ በጸዳ ክፍል ውስጥ እንደታሸገች ምትኖር ነበርች፡፡፣ ለብርሃንም ሆነ ለሌላ ጎጂ ነገር እራሷን በጭራሽ አታጋለጥም።ጁኒየር እናቱን ይወዳታል፣ ግን በደንብ እንዳልተንከባከባት ያውቃል፡፡
"ስለ እሷ ምን አሰብሽ?"ሲል ጠየቃት፡፡
"የሰሎሜን ሴት ልጅ ማለትህ ነው? ምንም እንኳን የእንደዚህ አይነት ደማቅ ሴት አድናቂ ባልሆንም በአካል በጣም ማራኪ ነች፣በእርግጥም እሷ በጣም ኃይለኛ ነች አይደል? ከእናቷ የበለጠ ቁም ነገር ያላት ትመስለኛለች… ሰሎሜ ትንሽ ደደብ ነገር ነበረች፣ እንደማስታውሰው ሁል ጊዜ ትስቅ ነበር።" ቆም ብላ ጭንቅላቷን ወደ አንድ ጎን ነቀነቀች፣ የሩቅ ሳቋን የምትሰማ ያህል ምታዳምጥ ትመስላለች። "ያህቺኛዋን ልጅ ግን ስትስቅ እንዳየኋት አላስታውስም።"
‹‹አዎ…በተወሰነ መልኩ ትክክል ነሽ››አላት
" ምስኪን የእኔ ልጅ እሷ ስትሞት በጣም ተጎድተህ እንደነበረ አውቃለሁ፣ የምትወደውን ሰው ማጣት ምን እንደሚመስል አውቃለሁ። ያ ባንተ ህይወት ውስጥ የተከሰተ ከባድ መከራ ነበር።››
‹‹አዎ እማዬ….በመሞቷ በጣም አዝኛለሁ››
በጣም ለስላሳ የነበረው ድምጿ በድንገት ተለወጠ። "ጁኒየር፣ በተለይ በሌሎች ሰዎች ፊት አባትህ እንዲያሳፍርህ መፍቀድ የለብህም።››ስትል ወደቀደመ ውይይታቸው መለሰችው፡፡
" ምንም ማለት አይደለም አባዬን ታውቂዋለሽ… ለክፋት ብሎ ሳይሆን ልማድ ሆኖበት ነው እንደዛ የተናገርኝ››
"እንዲህ እንድታስብ ነው የሚፈልገው። ሁል ጊዜ ለእሱ የብልግና ድርጊት ምክንያት እንድትፈልግለት ይፈልጋል። ፍሰሀ የሚያውቀው አንድ ድምፅ ብቻ ነው። ቁጣና ስድብ፡፡ልጄ እሱ እንደ እኛ ለስላሳ እና ገር መሆን አያውቅም። ልክ እንደ ገመዶ በሚገባው መንገድ ከእሱ ጋር መነጋገር አለብህ። ፍሰሀ አንተ ላይ በሚጮኸው መንገድ ገመዶን ሲያናግረው አይተህ ታውቃህ..?በፍፁም እሱን ደፍሮ አይዘረጥጠውም። ››
"አባዬ ገመዶ ምንም አይነት ስህተት እንደማይሰራ ያስባል። መላ ካምፓኒውን ከእኔ ይልቅ ኩማንደሩ ቢያስተዳድርለት ይመርጣል።አንድም ቀን በእኔ ስራ እርካታ ተሰምቶት አያውቅም››ብሎ በምሬት የተጠራቀመ ቅሬታውን ተናገረ፡፡
"ያ ፈፅሞ እውነት አይደለም!" ሳራ በሳምንታት ውስጥ ከነበራት የበለጠ ጠንካራ መንፈስ በማሳየት ተቃወመች። "ፍሰሀ በአንተ በጣም ይኮራብሃል። እንዴት ማሳየት እንዳለበት ግን አያውቅም። እሱ በጣም ከባድ ሰው ነው። በዙሪያው ያሉ ነገሮችን ሁሉ ለመቋጣጠር እንዲችል ሁሌ ጠንክራ እና ኮስታራ ሆኖ መታየት እዳለበት ነው የሚያምነው ። አንተም በእሱ መጠን ጠንካራ እንድትሆንለት ይፈልጋል።"
ጁኒየር ፈገግ አለ፣ "እሺ እናቴ፣ አሁን ወጣ ብዬ ራሴን ዘና ላድርግ…ነገ ጠዋት እየተንገዳገድኩ እመጣለሁ።››
ሳቀች ። በእሱ ፍቅር ውስጥ የተደበቀ ጥንካሬ እና ቀልድ ሁልጊዜ ያስደስታት ነበር። "ተስፋ አደርጋለሁ፣ ነገር ግን ጥንካሬ ፍሰሀ በአንተ ውስጥ ማየት የሚፈልገው መንፈስ ነው።››
ጁኒየር ‹‹ደህና እደሪ እማዬ››አለና ጎንበስ ብሎ ጉንጯን ሳመ፡፡
‹‹ቀስ ብለህ ንዳ..ደግሞ ብዙ እንዳትጠጣ ››የተለመደ የእናትነት ምክሯን ለገሰችው፡፡
እናቱን መኝታ ቤት ለቆ ወደሳሎን ሲመለስ አባቱን ምቹ ወንበሩ ላይ ቁጭ ብሎ ቢራውን እየተጎነጨ በሀሳብ ተውጦ አገኘው፡፡
"ያቺን ልጅ ወደዚህ ቤት ለማምጣት በአንተ ላይ መደገፍ እንደምችል አውቅ ነበር. እንደ አስብኩት ተሳክቷልሀል. የነበራትን ቁርጠኝነትና ጉጉት የሚሸረሽር ነገሮችን ማድረግ ችለናል.. ብልህ ከሆነች ብዙ ጉዳት ከመድረሱ በፊት ይህንን የጀመረችውን ነገር ታቆማለች..ደግሞ ብልህ ነችም ብዬ አስባለው፡፡››አለው
" ባታደርገውስ?"ጁኒዬር ጥርጣሬውን አነሳ፡፡
"እሷ ካላደረገች እኛም ያንን ድልድይ እናቋርጣለን" አለ አቶ ፍሰሀ።ከተቀመጠበት በመነሳት ፈገግ አለ እና በፍቅር ስሜት የጁኒየርን ጉንጩ ነካ በማድረግ "ደህና እደር ልጄ"ብሎ ወደመኝታ ቤቱ ተጓዘ፡፡
ጁኒየር አባቱ ወደመኝታው ሲሄድ ቆሞ ተመለከተው። በጣም ጥሩ ስሜት ስለተሰማው፣ በቆመበት ፈገግ አለ። አባቱ በእርሱ ቅር እንዳልተሰኘበት ገባው። ሴቶችን በማስተናገድ ረገድ የነበረው ልምድ በጣም የተዋጣለት ነበር። አለም የተረገመች ማራኪ ሴት ነበረች። አባቱ ባይነግረውም ኖሮ ለማንኛውም ያማልላት ነበር። ኮሪደሩን አቆርጦ ወደ ከፊት ለፊት በር ሲወጣ በመስታወት ውስጥ ለተመለከተው የገዛ ቆንጆ ቁመናው ሰላምታ ሰጠ።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
YouTube
አትሮኖስ_ Tube
Share your videos with friends, family, and the world
👍22❤18
ሀገር ማለት ሰው ነው ሰው ማለት ሀገ'ር
ከቶ ማይወስነው ዳርቻ ድንበር
ጥቅሳችን ነበር!
.
ጥያቄ1?
.
ሀገር ሰው ከሆነ በአፈር ማይለካ
የምንሰማው ሁሉ ካልሆነ ትረካ
ሀገር ሰው ከሆነ ድንበር ማይወስነው
ቃላችን የት ገባ? ከወዴት አደረስነው?
.
ጥያቄ2?
.
ለሰላም ለፍቅር ለህዝቦች ነፃነት
በዕኩልነት በፍቅር ቆመናል ባንድነት
መሰረተ ፅኑ ስብዕናን ያልሻርን
ህዝቦች ነን በስራ ለስራ የቆምን
.
ተንገዳግደን ሳለ ቆመናል እያልን
ተበታትነን ሳለ አበርን እያልን
በጠዋት ተነስተን ምንዘምረው ዲስኩር
እውነት ይገልፀናል? እስኪ በየት በኩል?
.
.
መልስ!!
.
........???.......
🔘ኪሩቤል አሰፋ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ከቶ ማይወስነው ዳርቻ ድንበር
ጥቅሳችን ነበር!
.
ጥያቄ1?
.
ሀገር ሰው ከሆነ በአፈር ማይለካ
የምንሰማው ሁሉ ካልሆነ ትረካ
ሀገር ሰው ከሆነ ድንበር ማይወስነው
ቃላችን የት ገባ? ከወዴት አደረስነው?
.
ጥያቄ2?
.
ለሰላም ለፍቅር ለህዝቦች ነፃነት
በዕኩልነት በፍቅር ቆመናል ባንድነት
መሰረተ ፅኑ ስብዕናን ያልሻርን
ህዝቦች ነን በስራ ለስራ የቆምን
.
ተንገዳግደን ሳለ ቆመናል እያልን
ተበታትነን ሳለ አበርን እያልን
በጠዋት ተነስተን ምንዘምረው ዲስኩር
እውነት ይገልፀናል? እስኪ በየት በኩል?
.
.
መልስ!!
.
........???.......
🔘ኪሩቤል አሰፋ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
YouTube
አትሮኖስ_ Tube
Share your videos with friends, family, and the world
👍3❤1
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ፡
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
///
እንደ ቤቱ ሁሉ በረቱም የተሠራው ከድንጋይ ነው። በረቶቹ በሁለት ረድፎች መተላለፊያ ተከፍለዋል በመደዳ ተደርድረዋል።በዚህ እርባታ ድርጅት የሚደልቡ ሰንጋዎች ቀጥታ ወደውጭ ገበያ ነው የሚቅርቡት፡፡ከላሞቹ የሚገኘው ወተት ግን እዛው ግቢ ውስጥ ባለ ፋብሪካ ተቀናብሮ እና ታሽጎ በዋናነት በሻሸመኔና ለአዋሳ ገበያ ይቀርባል፡፡ በግዙፉ ግቢ ውስጥ አንድ ኪሎ ሜትር ርቆ ግዙፍ የሆነ የእጨት መሰንጠቂያ ፋብሪካ የሚያሰማው ድምፅ ይሰማል፡፡ይሄ ጣውላ የሚመረትበት የእንጨት ፋብሪካ ነው፡፡ፋብሪካው የሚጠቀምበትን ጥሬ እቃ ከከተማዋ በቅርብ ኪሎ ሜትሮች ላይ ከሚገኝ ሶሌ ከሚባል ቀበሌ ላይ ከሚገኝ ግዙፍ ደን ነው የሚመጣው…ደኑም በአብዛኛው የአቶ ፍሰሀ የግል ሀብት ነው፡፡እናም ይህ ፋብሪካ በቀን ከ10 መኪና በላይ ጣውላ አምርቶ ወደ አዲስ አበባ እና የክልል ከተሞች ይልካል፡፡በተጨማሪም ከአካባቢው ከዚህ ፋብሪካ ወደ አፍንጫዋ የገባው የበሰበሰ ሳርና የእበት ሽታ በተወሰነ መጠን ረበሻት፡፡ በጸጥታ ወደዚያው አመራች፣ የተከፈተ ክፍል አልፋ ገበች። በአንድ ጊዜ ብዙ ፈረሶችን የሚለማመድበት ክብ ሜዳ አየች።ወዲያው ኩማንደር ገመዶ በጋጣው ውስጥ ካሉ ፈረሶች ጋር በቁጭት ሲያወራ ሰማች። ፈረሱ በርግጎ ለመውጣት ሞከረ።
"ተረጋጋ፣ተረጋጋ ››ይለዋል
"ምን ነካው?"ስትል ጠየቀችው…. ዞር ብሎ አላያትም ወይም ድምጿን በመስማቱ መገረሙን አላሳየም።
‹‹የምታምር ፈረስ ነች..ምን ሆና ነው?›› ስትል ሌላ ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
"ምንም አልሆነችም..ግን ሁሉ ጊዜ የሆነ ነገር እንደሆነች ማስመሰል ትወዳለች…እሷ ከእኔም ሆነ ከማንም በላይ ብልህ እንደሆነች ታስባለች።
እውነታው ግን አዎ እንደምታስበው በጣም ጎበዝ ነች ፤ ለሳዕታት ያለድካም በፍጥነት መጋለብ ትችላለች ፣ በውጤቱ መጨረሻ ግን መጎዳቷ አይቀርም።ስነግራት ስለማትሰማኝ..ስትጎዳም አታሳዝነኝም"አላት፡፡
እፍኝ እህል ዝቆ በውስጥ እጁ ላይ በማድረግ ፈረሱን እያበላው ነው።
"ይህ ለእኔ የተላለፈ ማጣቀሻ ነው አይደል? እንደ ማስፈራሪያ ልውሰደው?" ።” ስትል ጠየቀችው
ኮስተር ብሎ‹በፈለግሽው መንገድ መውሰድ ትችያለሽ››አለ
‹‹እሺ..ግን ታውቃለህ አይደል..?በጣም ትሁት የሆንክ ሰው ነህ››አለችው፡፡ የእሷን ስላቅ ችላ ብሎ"ስለ ፈረስ ብዙ አታውቂም አይደል?" ሲል ጠየቃት፡፡
"ግልፁን ለመናገር…አላውቅም" ብላ መለሰችለት።
"እዚህ ለመምጣት እንዴት አሰብሽ?"
"ጁኒየር ጋብዞኝ."
‹‹ጥሩ መራጭ ነሽ››
የአለም ደም በንዴት ተንተከተከ"የጁኒየር ወይም የሌላ የማንም ሰው አይደለሁም። እኔ እደምታስበው በቀላሉ የምዘገን ሴት አይደለሁም።››
ጀርባውን አዙሮ ወደ ተቃራኒው የሕንፃው ጫፍ ተራመደ"ቆይ! ጥቂት ጥያቄዎችን ልጠይቅህ እፈልጋለሁ።"አለችው
"ጠይቂኝ"
"ገመዶ…እባክህ ከስራ ውጪ በሆኑ ጉዳዬች ላይ ማውራት እፈልጋለሁ ። የራሴን የማወቅ ጉጉት ለማርካት ነው" አለችው::
"ቴክኒኩን አውቀዋለሁ አቃቢ ህግ፡፡ እኔ እራሴ ብዙ ጊዜ ተጠቅሜበታለሁ። አንቺ ከተጠርጣሪው ጋር በቸልተኝነት ትጫወቻለሽ፣ በመዘናጋት ሊደብቀው የፈለገውን ነገር ዘርግፎ ይነግርሻል…ከዛ መራጃሽን ታጠናክሪያለሽ ።"
"እንደዚያ አይደለም ማውራት ብቻ ነው የምፈልገው."
"ስለ ምን?"
"ስለ ሶሌዎች "
"ስለ እነሱ?"
እግሩን አንፈርክኮ ቆመና፣ እጆቹን ወደ ጂንሱ የኋላ ኪስ ውስጥ አስገባ ፣ አቋሙ የሚያስፈራራ ወንድ ሆኖ ነው የተሰማት። እያናደዳት ቢሆንም ስሜቷን ቀስቅሷታል።
"ፍሰሀ እና ሳራ ደስተኛ ትዳር ያላቸው ይመስልሀል?"
ጥያቄዋ ከጠበቀው ውጭ ስለሆነበት ዓይን ዓይኗን እያየ "ምን?"ሲል አፈጠጠባት፡፡ "እንዲዚህ አትየኝ ፡ የምጠይቀው የአንተን አስተያየት እንጂ ሞያዊ ትንታኔ አይደለም።" "በእግዚያብሄር ስም … ልዩነት ምንድነው?"
"ሳራ ጆ…. ፍሰሀ እንዲያገባት የምጠብቃት አይነት ሴት አይደለችም …ለዛ ነው የጠየቅኩህ።"
"ስለ ጉዳዩ አስቤበት አላውቅም." " አብረው ይተኛሉ ?››
‹‹ በአልጋ ላይ የሚያደርጉት ወይም የማያደርጉት ነገር የኔ ጉዳይ አይደለም። በተጨማሪም
፣ ግድ የለኝም። ››
"እሺ…አቶ ፍሰሀ ሌሎች ሴቶችን ጋር ይሄዳል?"
ከጥቋቁር ዓይኖቹ ጀርባ ብስጭት ተመለከተች። ከእሷ ጋር ያለው ትዕግስት እየተሟጠጠ ነበር።
"ሳራ ጆን እንደ ስሜታዊ ሴት ነው የምታስቢያት?"
"አይ" አለም መለሰች።"ጋሽ ፍሰሀ ጤናማ የወሲብ ፍላጎት አለው ብለህ ታስባለህ?" "እንደ ምግብ ፍላጎቶቹ ከሆነ አዎ እንደዛ አስባለው።"
"ግንኙነታቸው ጁኒየር ላይ ተጽዕኖ አሳድሯል?"
"እንዴት ያንን ማወቅ እችላለው? እሱን ጠይቀው።" "እሱንም መጠየቄ አይቀርም፡፡››
"አንቺን በማይመለከትሽ ጉዳይ ላይ ጣልቃ እየገባሽ እንደሆነ የሚነግርሽ ሰው መኖር አለበት››
የሱ ስላቅ እንዲያስፈራራት አልፈቀደችም።"የወላጆቹ ግንኙነት ጁኒየር ለሶስት ያልተሳካ ትዳር ዳርጎታል… ለምን እንደሆነ ታብራራልኛለህ? ››
‹‹ይህ አንቺን የሚመለከት ጉዳይ አይደለም…አልኩሽ እኮ!!››
"የእኔ ጉዳይ ነው."ፍርጥም ብላ መለሰችለት፡፡
"እንዴት? "
‹‹ምክንያቱም ጁኒየር እናቴን ይወዳት ስለነበረ።››ቃላቱ በእርጋታ ከአንደበቷ ወጡ ፡፡
የኩማደሩ ኮስታራ ፊት የበለጠ ተኮሰታተረ ፡፡ ‹‹ማን ነገረሽ?››
‹‹ሁለታችሁም እንደምትወዷት ነግሮኛል።››
ለረጅም ጊዜ አፈጠጠባት፣ ከዚያም ትከሻውን ነቀነቀና ‹‹በአንድ ወይም በሌላ መንገድ እንወዳት ነበር…ታዲያ ምን ይጠበስ.?››
"ለዚህ ነው የጁኒየር ትዳሮች ያልሰሩት? አሁንም እናቴን በልቡ ታቅፎ ይዞ ስላለ ነው?"
" እዚህ ጉዳይ ላይ ምን አይነት አስተያየት መስጠት አልችልም."
‹‹እባክህ››
"ሰሎሜ ከጁኒየር ትዳሮች ጋር ምንም ግንኙነት ያላት አይመስለኝም። የጥፋተኝነት ስሜት ሳይሰማው በየመዝናኛ ስፍራው ከሚያገኛቸው ሴቶች ጋር ለመቅበጥ እንዲችል በየተወሰነ ዓመት ሚስቶቹን ይፈታል ።የእኔ ግምት ይሄ ነው፡፡››
የሰጠው መግለጫ እሷን ለማስከፋት ታስቦ ነበር, እናም ተሳክቶለታል፡፡ ቢሆንም ምን ያህል እንዳበሳጫት ላለማሳየት ሞከረች።
"በዚህ ጉዳይ የጥፋተኝነት ስሜት የሚሰማው ለምን ይመስልሃል?" "ጄኔቲክስ. ምን አልባት ከእናቱ የወረሰው ለስላሳ ባህሪ ይመስለኛል››
"አንተስ?"
"የማደርገው ማንኛውንም ነገር አስቤና ተጨንቄ ስለማደርገው የጥፋተኝነት ስሜት አይሰማኝም."
"ግድያ ቢሆንም እንኳን?"
ፈገግታው ጠፋ እና ዓይኖቹን ጨፈነ። "አግብተህ ታውቃለህ?"
"አይ።"
"ለምን ሳታገባም?"
‹‹ማግባት እኮ ሀይማኖታዊ ግዳጅ አይደለም …ይሄ የፍላጎት ጉዳይ ነው…ልክ እንደአንቺ ማለት ነው››
‹‹ገባኝ። እስኪ ስለ አባትህ ንገረኝ?" ቀስ በቀስ ኩማደሩ ፈረሶቹ ወደሚዝናኑበት ሜዳ ተጠጋ
….እሷም ከኃላ ከኃላ እተከተለችው ነው። ጠንከር ባለ ቀዝቃዛ እይታ ተመለከታት።
አለም "አባትህ ገና ትምህርት ቤት እያለህ እንደሞተ አውቃለሁ። ጁኒየር ዛሬ ነግሮኛል። ከሞተ በኃላ እዚህ ከነጁኒዬር ጋር ለመኖር መጣህ።"
‹‹አለም… ስለማወራው ነገር የማወቅ ጉጉት አለሽ?።"
"የማወቅ ጉጉት የለኝም። ከምርመራዬ ጋር የተያያዙ እውነታዎችን እየፈለግኩ ነው።››
"ኦህ፣ እርግጠኛ ነሽ?እንደ ጋሽ ፍሰሀ የወሲብ ሕይወት ያሉ ተዛማጅ ነገሮች ለምርመራሽ ስለምትፈልጊያቸው ነው የምትቆፍሪው?።››
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ፡
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
///
እንደ ቤቱ ሁሉ በረቱም የተሠራው ከድንጋይ ነው። በረቶቹ በሁለት ረድፎች መተላለፊያ ተከፍለዋል በመደዳ ተደርድረዋል።በዚህ እርባታ ድርጅት የሚደልቡ ሰንጋዎች ቀጥታ ወደውጭ ገበያ ነው የሚቅርቡት፡፡ከላሞቹ የሚገኘው ወተት ግን እዛው ግቢ ውስጥ ባለ ፋብሪካ ተቀናብሮ እና ታሽጎ በዋናነት በሻሸመኔና ለአዋሳ ገበያ ይቀርባል፡፡ በግዙፉ ግቢ ውስጥ አንድ ኪሎ ሜትር ርቆ ግዙፍ የሆነ የእጨት መሰንጠቂያ ፋብሪካ የሚያሰማው ድምፅ ይሰማል፡፡ይሄ ጣውላ የሚመረትበት የእንጨት ፋብሪካ ነው፡፡ፋብሪካው የሚጠቀምበትን ጥሬ እቃ ከከተማዋ በቅርብ ኪሎ ሜትሮች ላይ ከሚገኝ ሶሌ ከሚባል ቀበሌ ላይ ከሚገኝ ግዙፍ ደን ነው የሚመጣው…ደኑም በአብዛኛው የአቶ ፍሰሀ የግል ሀብት ነው፡፡እናም ይህ ፋብሪካ በቀን ከ10 መኪና በላይ ጣውላ አምርቶ ወደ አዲስ አበባ እና የክልል ከተሞች ይልካል፡፡በተጨማሪም ከአካባቢው ከዚህ ፋብሪካ ወደ አፍንጫዋ የገባው የበሰበሰ ሳርና የእበት ሽታ በተወሰነ መጠን ረበሻት፡፡ በጸጥታ ወደዚያው አመራች፣ የተከፈተ ክፍል አልፋ ገበች። በአንድ ጊዜ ብዙ ፈረሶችን የሚለማመድበት ክብ ሜዳ አየች።ወዲያው ኩማንደር ገመዶ በጋጣው ውስጥ ካሉ ፈረሶች ጋር በቁጭት ሲያወራ ሰማች። ፈረሱ በርግጎ ለመውጣት ሞከረ።
"ተረጋጋ፣ተረጋጋ ››ይለዋል
"ምን ነካው?"ስትል ጠየቀችው…. ዞር ብሎ አላያትም ወይም ድምጿን በመስማቱ መገረሙን አላሳየም።
‹‹የምታምር ፈረስ ነች..ምን ሆና ነው?›› ስትል ሌላ ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
"ምንም አልሆነችም..ግን ሁሉ ጊዜ የሆነ ነገር እንደሆነች ማስመሰል ትወዳለች…እሷ ከእኔም ሆነ ከማንም በላይ ብልህ እንደሆነች ታስባለች።
እውነታው ግን አዎ እንደምታስበው በጣም ጎበዝ ነች ፤ ለሳዕታት ያለድካም በፍጥነት መጋለብ ትችላለች ፣ በውጤቱ መጨረሻ ግን መጎዳቷ አይቀርም።ስነግራት ስለማትሰማኝ..ስትጎዳም አታሳዝነኝም"አላት፡፡
እፍኝ እህል ዝቆ በውስጥ እጁ ላይ በማድረግ ፈረሱን እያበላው ነው።
"ይህ ለእኔ የተላለፈ ማጣቀሻ ነው አይደል? እንደ ማስፈራሪያ ልውሰደው?" ።” ስትል ጠየቀችው
ኮስተር ብሎ‹በፈለግሽው መንገድ መውሰድ ትችያለሽ››አለ
‹‹እሺ..ግን ታውቃለህ አይደል..?በጣም ትሁት የሆንክ ሰው ነህ››አለችው፡፡ የእሷን ስላቅ ችላ ብሎ"ስለ ፈረስ ብዙ አታውቂም አይደል?" ሲል ጠየቃት፡፡
"ግልፁን ለመናገር…አላውቅም" ብላ መለሰችለት።
"እዚህ ለመምጣት እንዴት አሰብሽ?"
"ጁኒየር ጋብዞኝ."
‹‹ጥሩ መራጭ ነሽ››
የአለም ደም በንዴት ተንተከተከ"የጁኒየር ወይም የሌላ የማንም ሰው አይደለሁም። እኔ እደምታስበው በቀላሉ የምዘገን ሴት አይደለሁም።››
ጀርባውን አዙሮ ወደ ተቃራኒው የሕንፃው ጫፍ ተራመደ"ቆይ! ጥቂት ጥያቄዎችን ልጠይቅህ እፈልጋለሁ።"አለችው
"ጠይቂኝ"
"ገመዶ…እባክህ ከስራ ውጪ በሆኑ ጉዳዬች ላይ ማውራት እፈልጋለሁ ። የራሴን የማወቅ ጉጉት ለማርካት ነው" አለችው::
"ቴክኒኩን አውቀዋለሁ አቃቢ ህግ፡፡ እኔ እራሴ ብዙ ጊዜ ተጠቅሜበታለሁ። አንቺ ከተጠርጣሪው ጋር በቸልተኝነት ትጫወቻለሽ፣ በመዘናጋት ሊደብቀው የፈለገውን ነገር ዘርግፎ ይነግርሻል…ከዛ መራጃሽን ታጠናክሪያለሽ ።"
"እንደዚያ አይደለም ማውራት ብቻ ነው የምፈልገው."
"ስለ ምን?"
"ስለ ሶሌዎች "
"ስለ እነሱ?"
እግሩን አንፈርክኮ ቆመና፣ እጆቹን ወደ ጂንሱ የኋላ ኪስ ውስጥ አስገባ ፣ አቋሙ የሚያስፈራራ ወንድ ሆኖ ነው የተሰማት። እያናደዳት ቢሆንም ስሜቷን ቀስቅሷታል።
"ፍሰሀ እና ሳራ ደስተኛ ትዳር ያላቸው ይመስልሀል?"
ጥያቄዋ ከጠበቀው ውጭ ስለሆነበት ዓይን ዓይኗን እያየ "ምን?"ሲል አፈጠጠባት፡፡ "እንዲዚህ አትየኝ ፡ የምጠይቀው የአንተን አስተያየት እንጂ ሞያዊ ትንታኔ አይደለም።" "በእግዚያብሄር ስም … ልዩነት ምንድነው?"
"ሳራ ጆ…. ፍሰሀ እንዲያገባት የምጠብቃት አይነት ሴት አይደለችም …ለዛ ነው የጠየቅኩህ።"
"ስለ ጉዳዩ አስቤበት አላውቅም." " አብረው ይተኛሉ ?››
‹‹ በአልጋ ላይ የሚያደርጉት ወይም የማያደርጉት ነገር የኔ ጉዳይ አይደለም። በተጨማሪም
፣ ግድ የለኝም። ››
"እሺ…አቶ ፍሰሀ ሌሎች ሴቶችን ጋር ይሄዳል?"
ከጥቋቁር ዓይኖቹ ጀርባ ብስጭት ተመለከተች። ከእሷ ጋር ያለው ትዕግስት እየተሟጠጠ ነበር።
"ሳራ ጆን እንደ ስሜታዊ ሴት ነው የምታስቢያት?"
"አይ" አለም መለሰች።"ጋሽ ፍሰሀ ጤናማ የወሲብ ፍላጎት አለው ብለህ ታስባለህ?" "እንደ ምግብ ፍላጎቶቹ ከሆነ አዎ እንደዛ አስባለው።"
"ግንኙነታቸው ጁኒየር ላይ ተጽዕኖ አሳድሯል?"
"እንዴት ያንን ማወቅ እችላለው? እሱን ጠይቀው።" "እሱንም መጠየቄ አይቀርም፡፡››
"አንቺን በማይመለከትሽ ጉዳይ ላይ ጣልቃ እየገባሽ እንደሆነ የሚነግርሽ ሰው መኖር አለበት››
የሱ ስላቅ እንዲያስፈራራት አልፈቀደችም።"የወላጆቹ ግንኙነት ጁኒየር ለሶስት ያልተሳካ ትዳር ዳርጎታል… ለምን እንደሆነ ታብራራልኛለህ? ››
‹‹ይህ አንቺን የሚመለከት ጉዳይ አይደለም…አልኩሽ እኮ!!››
"የእኔ ጉዳይ ነው."ፍርጥም ብላ መለሰችለት፡፡
"እንዴት? "
‹‹ምክንያቱም ጁኒየር እናቴን ይወዳት ስለነበረ።››ቃላቱ በእርጋታ ከአንደበቷ ወጡ ፡፡
የኩማደሩ ኮስታራ ፊት የበለጠ ተኮሰታተረ ፡፡ ‹‹ማን ነገረሽ?››
‹‹ሁለታችሁም እንደምትወዷት ነግሮኛል።››
ለረጅም ጊዜ አፈጠጠባት፣ ከዚያም ትከሻውን ነቀነቀና ‹‹በአንድ ወይም በሌላ መንገድ እንወዳት ነበር…ታዲያ ምን ይጠበስ.?››
"ለዚህ ነው የጁኒየር ትዳሮች ያልሰሩት? አሁንም እናቴን በልቡ ታቅፎ ይዞ ስላለ ነው?"
" እዚህ ጉዳይ ላይ ምን አይነት አስተያየት መስጠት አልችልም."
‹‹እባክህ››
"ሰሎሜ ከጁኒየር ትዳሮች ጋር ምንም ግንኙነት ያላት አይመስለኝም። የጥፋተኝነት ስሜት ሳይሰማው በየመዝናኛ ስፍራው ከሚያገኛቸው ሴቶች ጋር ለመቅበጥ እንዲችል በየተወሰነ ዓመት ሚስቶቹን ይፈታል ።የእኔ ግምት ይሄ ነው፡፡››
የሰጠው መግለጫ እሷን ለማስከፋት ታስቦ ነበር, እናም ተሳክቶለታል፡፡ ቢሆንም ምን ያህል እንዳበሳጫት ላለማሳየት ሞከረች።
"በዚህ ጉዳይ የጥፋተኝነት ስሜት የሚሰማው ለምን ይመስልሃል?" "ጄኔቲክስ. ምን አልባት ከእናቱ የወረሰው ለስላሳ ባህሪ ይመስለኛል››
"አንተስ?"
"የማደርገው ማንኛውንም ነገር አስቤና ተጨንቄ ስለማደርገው የጥፋተኝነት ስሜት አይሰማኝም."
"ግድያ ቢሆንም እንኳን?"
ፈገግታው ጠፋ እና ዓይኖቹን ጨፈነ። "አግብተህ ታውቃለህ?"
"አይ።"
"ለምን ሳታገባም?"
‹‹ማግባት እኮ ሀይማኖታዊ ግዳጅ አይደለም …ይሄ የፍላጎት ጉዳይ ነው…ልክ እንደአንቺ ማለት ነው››
‹‹ገባኝ። እስኪ ስለ አባትህ ንገረኝ?" ቀስ በቀስ ኩማደሩ ፈረሶቹ ወደሚዝናኑበት ሜዳ ተጠጋ
….እሷም ከኃላ ከኃላ እተከተለችው ነው። ጠንከር ባለ ቀዝቃዛ እይታ ተመለከታት።
አለም "አባትህ ገና ትምህርት ቤት እያለህ እንደሞተ አውቃለሁ። ጁኒየር ዛሬ ነግሮኛል። ከሞተ በኃላ እዚህ ከነጁኒዬር ጋር ለመኖር መጣህ።"
‹‹አለም… ስለማወራው ነገር የማወቅ ጉጉት አለሽ?።"
"የማወቅ ጉጉት የለኝም። ከምርመራዬ ጋር የተያያዙ እውነታዎችን እየፈለግኩ ነው።››
"ኦህ፣ እርግጠኛ ነሽ?እንደ ጋሽ ፍሰሀ የወሲብ ሕይወት ያሉ ተዛማጅ ነገሮች ለምርመራሽ ስለምትፈልጊያቸው ነው የምትቆፍሪው?።››
❤47👍8
"ያ እኔ የምከተለው የምርመራ መንገድ ነው፣ ኩማንደር ። እንደህግ ኦፊሰርነትህ ያንን መለየት ትችላለህ፣ አይደል? ››
ዓይኖቹ ይበልጥ ቀዝቃዛ ሆነዋል… ምንም ለመናገር ፍላጎት ያለው አይመስልም "እናቴ በሞተችበት ምሽት ምን እንደተከሰተ ማወቅ እፈልጋለው?"ስትል ጥያቄዋን ቀጠለች፡፡
" ይህ በሬ ወለደ ነው…ያንቺ ፍላጎት ከሽማግሌዬ ጋር ምን አገናኘው?"
"ምናልባት ምንም የሚያገናኘው ነገር የለም ይሆናል ፣ ግን አንተ ንገረኝ ። ምንም ችግር ከሌለው ስለሱ መናገር ለምን ትፈራለህ ?"››
"ጁኒየር የኔ አባት እንዴት እንደሞተ ነግሮሃሻል?"
ጭንቅላቷን በአሉታ ነቀነቀች። ኩማደር መራራ ሳቅ ሳቀ ‹‹ለምን ስለአባቴ ማውራት እንደማልፈልግ መገመት አትችይም. ?››ፊት ለፊቷ ቆመና ዓይን ዓይኗን እያየ
"እሺ መስማት ከፈለግሽ ልንገርሽ…አባቴ የራሱ ትውከት አንቆት ነው የሞተው፣ ራሱን ለማዳን እስኪያቅተው ድረስ ሰክሮ ነበር። በጣም የሚያስደነግጥ ነበር፣ በተለይ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርእሰ መምህር ከክፍል አስጠርቶኝ አባቴ መሞቱን ሲነግረኝ የተሰማኝን መገመት አትችይም፡፡"
"ገመዶ…በጣም አዝናለው" አለም እጇን አነሳች እና እጇቹን ያዘች። ወደ ጎን ገሸሽ አደረገው እና ንግግሩን ቀጠለ"አባቴ የከተማው ሰካራምና፣ መሳቂያ፣ ዋጋ የሌለው ሰው ነበር። መሞቱን ስሰማ አላለቀስኩም ነበር።እንደውም ደስ ብሎኝ ነበር። እሱ ብኩን ሰው ነበር። አንድም የጽድቅ ስራ ሰርቷ የማያውቅ ጨካኝ የቁጭት ልጅ ነበር…ለእኔ አባቴ ነው ብዬ መጥራት ያሳፍረኛል ። ለእሱ እኔም ተጠያቂ ነበርኩ. እንደ ሞኝ፣ ቤተሰብ መሆናችንን እሰብኩ እና እያስመሰልኩ ነበር። እኔ ኳስ ስጫወት ለማየት እንዲመጣ ሁል ጊዜ እጨቀጭቀው ነበር ፡፡አንድ ቀን እንደምንም ብሎ በጨዋታው ቦታ ተገኘ ። ግን አስጠይ ትዕይንት ነበር የተፈጠረው፣ ሰክሮ ስለመጣ አንዴ ሲወድቅ አንዴ ደግሞ ባነር እያፈረሰ በመረበሽ ቦታውን አተረማመሰው…በወቅቱ በሃፍረት ልሞት ደርሼ ነበር። ዳግመኛ እንዳይመጣ ነገርኩት፤ ጠላሁት፤ተጠላን›› ሲል ነገራት፡፡
አለም ይህን የሚያቃጥል ቁስሉን እንዲያስታውስ ስላስገደደችው ተጸጸተች፤ ነገር ግን በነጻነት መናገር በመቻሉ ተደሰተች። የልጅነት ህይወቱ ስለ ሰውዬው ብዙ ነገር እንድትገነዘብ እረድቷታል፡፡እሱ በልጅነቱ ተገልሎ በበደል ስለኖረ ሰው እየገለፀ ነበር፣ ፡፡
"አንተ ልጅ እያለህ በትምህርት ቤት ጥሩ መሪ እንደሆንክ ተነግሮኛል፣››
" ያ ..ከፊል እውነት ነው…ትምህርት ቤት ከሰሎሜ በስተቀር ሌሎች ልጆች ሁሉም ያሾፉብኝ ነበር…. ከዚያም ከፍ እያልኩ ስሄድ መፋለምን መቧቀስ ተማርኩኝ…. ልጆች በእኔ ላይ ማሾፍና መሳቅ አቆሙ…. ሁሉም ልጆች ጠላቴ ከሚሆኑ ይልቅ ጓደኛዬ ቢሆኑ እንደሚሻል ተገነዘቡ ."ከንፈሩ በንቀት ጠመዘዘና ትንፋሽ ወስዶ ንግግሩን አራዘመ"ወይዘሪት አቃቤ ህግ፣ እኔ ሌባ ነበርኩ። ልበላው የምችለውን ማንኛውንም ነገር ሰርቄ ነበር የማገኘው….መዋያዬ አቦስቶና አራዳ ነበር፡፡ ››
የምትለው ነገር አልነበራትም። እሱም እንደማይኖራት ያውቅ ነበር። ለዛ ነው የነገራት። ፣ምንም እንኳን እሷ የምትቀምሰው ምግብ አጥታ ባታውቅም የልጅነት ጊዜያቸው ብዙም ልዩነት እንደሌለው አላወቀም። አያቷ ለአካላዊ ፍላጎቶቿ ለሟሟላት ችላ ነበር ፣ነገር ግን የስሜት ስንጥቆቾ ሁል ግዜም ክፍት ነበሩ ። አለም የበታችነት ስሜት እየተሰማት እና እንደማትወደድ እያሰበች ነበር ያደገችው።
በስሜታዊነት "ይቅርታ ገመዶ›› አለችው፡፡
‹‹ትእይንቱ ከተፈፀመ ቆይቷል…. አሁን ምንም አይነት ርህራሄ አልፈልግም …ያ ያሳለፍኩት ህይወት ጠንካራና እና ጨካኝ አድርጎኛል፣ እና እንደዛ በመሆኔ ደግሞ ወድጄዋለሁ። ለራሴ መቆምን ቀደም ብዬ ተምሬያለሁ፡፡ ምክንያቱም በእርግጠኝነት ማንም ሊጋፈጠኝ እንደማይደፍር እርግጠኛ ነበርኩ። ከራሴ በቀር በማንም ላይ አልመካም፣ በተለይ ወደ ሽማግሌው አባቴ ደረጃ ዝቅ ማለት እንደሌለብኝ ልጅ ሆኜ ነበር ራሴን ያሳመንኩት።››
"እና ያንን ተግባራዊ ለማድረግ ጠንክረህ ሰራህ …አይደል? …በጣም ስሜታዊ ነህ።"
"ሰዎች… ያ ሽማጊሌ አባቴን እንደነበረ እንዲረሱት እፈልጋለሁ።ማንም ከእኔ ጋር እንዲያገናኘው አልፈልግም። መቼም።››ጥርሱን አንቀጫቀጨ እና ያቋረጠውን ንግግር ቀጠለ "ለአርባ ሦስት ዓመታት ያህል የእሱ ልጅ በመሆኔ በሀዘን አሳልፌያለሁ። አሁን ሰዎች ሊረሱት ሲሉ፣ አንቺ መጥተሽ የማያስደስት ጥያቄዎችን መጠየቅ ጀምረሻል፣ የሞቱ ጉዳዮችን እያነሳሽ ነው፣ ለሁሉንም ሰው እኔ የዛ ሰውዬ ልጅ እንደሆንኩ እያስታወሻቸው ነው። እኔ ወዳለሁበት ለመድረስ ከጉድጓድ ውስጥ ወጣሁ…በጠንካራ ግፊት ወደ ኋላ ጎትተሸ ልትመልሺኝ እየሞከርሽ ነው። ››
" እርግጠኛ ነኝ የአባትህን ጥፋት ማንም በአንተ ላይ ለማላከክ አይደፍርም ።"
‹‹እንደዛ ይመስልሻል? በራስሽ ሲደርስ በቅርብ ትረጂዋለሽ… ምክንያቱም አንቺን ከሰሎሜ ጋር ማወዳደር ይጀምራሉ."
"ያ አያስጨንቀኝም። ንጽጽሮችን እቀበላለሁ።"
"እርግጠኛ ነሽ?"
" ማለት?"
"እናትሽ ..ቅድስት አልነበረችም."
" እኔም ትሆናለች ብዬ ጠብቄ አላውቅም."
"ምናባዊ እናት በራስሽ አእምሮ ውስጥ የፈጠርሽ ይመስለኛል እና ሰሎሜ ያንን ክፍተት እንድትሞላልሽ እየጠበቅሽ ነው."
"ይህ አስቂኝ ነው….ግን እንዳስጠነቀቅኩሽ አስታውሺ" አለ በለሆሳስ።ትንፋሽ ወሰደና ንግግሩን ቀጠለ "ወደ አዲስ አበባሽ ተመለሺ፣ በዲዛይነር የተሰሩ ቅንጡ ልብሶችህን እና መግለጫዎችሽን የሆኑትን አጭር ቀሚስ እየለበሽ ዘና በይ። ያለፈውን ትተሽ ሂጂ፡፡ እዚህ ያለ ማንም ሰው በሰሎሜ ላይ የተፈጠረውን ያለፈውን ጊዜ ታሪክ ማስታወስ አይፈልግም… በዚህ ጊቢ በረት ውስጥ የሞተችው ሰሎሜ እንደሞተች በሰላም ብንተዋት ይሻላል"አላት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ዓይኖቹ ይበልጥ ቀዝቃዛ ሆነዋል… ምንም ለመናገር ፍላጎት ያለው አይመስልም "እናቴ በሞተችበት ምሽት ምን እንደተከሰተ ማወቅ እፈልጋለው?"ስትል ጥያቄዋን ቀጠለች፡፡
" ይህ በሬ ወለደ ነው…ያንቺ ፍላጎት ከሽማግሌዬ ጋር ምን አገናኘው?"
"ምናልባት ምንም የሚያገናኘው ነገር የለም ይሆናል ፣ ግን አንተ ንገረኝ ። ምንም ችግር ከሌለው ስለሱ መናገር ለምን ትፈራለህ ?"››
"ጁኒየር የኔ አባት እንዴት እንደሞተ ነግሮሃሻል?"
ጭንቅላቷን በአሉታ ነቀነቀች። ኩማደር መራራ ሳቅ ሳቀ ‹‹ለምን ስለአባቴ ማውራት እንደማልፈልግ መገመት አትችይም. ?››ፊት ለፊቷ ቆመና ዓይን ዓይኗን እያየ
"እሺ መስማት ከፈለግሽ ልንገርሽ…አባቴ የራሱ ትውከት አንቆት ነው የሞተው፣ ራሱን ለማዳን እስኪያቅተው ድረስ ሰክሮ ነበር። በጣም የሚያስደነግጥ ነበር፣ በተለይ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርእሰ መምህር ከክፍል አስጠርቶኝ አባቴ መሞቱን ሲነግረኝ የተሰማኝን መገመት አትችይም፡፡"
"ገመዶ…በጣም አዝናለው" አለም እጇን አነሳች እና እጇቹን ያዘች። ወደ ጎን ገሸሽ አደረገው እና ንግግሩን ቀጠለ"አባቴ የከተማው ሰካራምና፣ መሳቂያ፣ ዋጋ የሌለው ሰው ነበር። መሞቱን ስሰማ አላለቀስኩም ነበር።እንደውም ደስ ብሎኝ ነበር። እሱ ብኩን ሰው ነበር። አንድም የጽድቅ ስራ ሰርቷ የማያውቅ ጨካኝ የቁጭት ልጅ ነበር…ለእኔ አባቴ ነው ብዬ መጥራት ያሳፍረኛል ። ለእሱ እኔም ተጠያቂ ነበርኩ. እንደ ሞኝ፣ ቤተሰብ መሆናችንን እሰብኩ እና እያስመሰልኩ ነበር። እኔ ኳስ ስጫወት ለማየት እንዲመጣ ሁል ጊዜ እጨቀጭቀው ነበር ፡፡አንድ ቀን እንደምንም ብሎ በጨዋታው ቦታ ተገኘ ። ግን አስጠይ ትዕይንት ነበር የተፈጠረው፣ ሰክሮ ስለመጣ አንዴ ሲወድቅ አንዴ ደግሞ ባነር እያፈረሰ በመረበሽ ቦታውን አተረማመሰው…በወቅቱ በሃፍረት ልሞት ደርሼ ነበር። ዳግመኛ እንዳይመጣ ነገርኩት፤ ጠላሁት፤ተጠላን›› ሲል ነገራት፡፡
አለም ይህን የሚያቃጥል ቁስሉን እንዲያስታውስ ስላስገደደችው ተጸጸተች፤ ነገር ግን በነጻነት መናገር በመቻሉ ተደሰተች። የልጅነት ህይወቱ ስለ ሰውዬው ብዙ ነገር እንድትገነዘብ እረድቷታል፡፡እሱ በልጅነቱ ተገልሎ በበደል ስለኖረ ሰው እየገለፀ ነበር፣ ፡፡
"አንተ ልጅ እያለህ በትምህርት ቤት ጥሩ መሪ እንደሆንክ ተነግሮኛል፣››
" ያ ..ከፊል እውነት ነው…ትምህርት ቤት ከሰሎሜ በስተቀር ሌሎች ልጆች ሁሉም ያሾፉብኝ ነበር…. ከዚያም ከፍ እያልኩ ስሄድ መፋለምን መቧቀስ ተማርኩኝ…. ልጆች በእኔ ላይ ማሾፍና መሳቅ አቆሙ…. ሁሉም ልጆች ጠላቴ ከሚሆኑ ይልቅ ጓደኛዬ ቢሆኑ እንደሚሻል ተገነዘቡ ."ከንፈሩ በንቀት ጠመዘዘና ትንፋሽ ወስዶ ንግግሩን አራዘመ"ወይዘሪት አቃቤ ህግ፣ እኔ ሌባ ነበርኩ። ልበላው የምችለውን ማንኛውንም ነገር ሰርቄ ነበር የማገኘው….መዋያዬ አቦስቶና አራዳ ነበር፡፡ ››
የምትለው ነገር አልነበራትም። እሱም እንደማይኖራት ያውቅ ነበር። ለዛ ነው የነገራት። ፣ምንም እንኳን እሷ የምትቀምሰው ምግብ አጥታ ባታውቅም የልጅነት ጊዜያቸው ብዙም ልዩነት እንደሌለው አላወቀም። አያቷ ለአካላዊ ፍላጎቶቿ ለሟሟላት ችላ ነበር ፣ነገር ግን የስሜት ስንጥቆቾ ሁል ግዜም ክፍት ነበሩ ። አለም የበታችነት ስሜት እየተሰማት እና እንደማትወደድ እያሰበች ነበር ያደገችው።
በስሜታዊነት "ይቅርታ ገመዶ›› አለችው፡፡
‹‹ትእይንቱ ከተፈፀመ ቆይቷል…. አሁን ምንም አይነት ርህራሄ አልፈልግም …ያ ያሳለፍኩት ህይወት ጠንካራና እና ጨካኝ አድርጎኛል፣ እና እንደዛ በመሆኔ ደግሞ ወድጄዋለሁ። ለራሴ መቆምን ቀደም ብዬ ተምሬያለሁ፡፡ ምክንያቱም በእርግጠኝነት ማንም ሊጋፈጠኝ እንደማይደፍር እርግጠኛ ነበርኩ። ከራሴ በቀር በማንም ላይ አልመካም፣ በተለይ ወደ ሽማግሌው አባቴ ደረጃ ዝቅ ማለት እንደሌለብኝ ልጅ ሆኜ ነበር ራሴን ያሳመንኩት።››
"እና ያንን ተግባራዊ ለማድረግ ጠንክረህ ሰራህ …አይደል? …በጣም ስሜታዊ ነህ።"
"ሰዎች… ያ ሽማጊሌ አባቴን እንደነበረ እንዲረሱት እፈልጋለሁ።ማንም ከእኔ ጋር እንዲያገናኘው አልፈልግም። መቼም።››ጥርሱን አንቀጫቀጨ እና ያቋረጠውን ንግግር ቀጠለ "ለአርባ ሦስት ዓመታት ያህል የእሱ ልጅ በመሆኔ በሀዘን አሳልፌያለሁ። አሁን ሰዎች ሊረሱት ሲሉ፣ አንቺ መጥተሽ የማያስደስት ጥያቄዎችን መጠየቅ ጀምረሻል፣ የሞቱ ጉዳዮችን እያነሳሽ ነው፣ ለሁሉንም ሰው እኔ የዛ ሰውዬ ልጅ እንደሆንኩ እያስታወሻቸው ነው። እኔ ወዳለሁበት ለመድረስ ከጉድጓድ ውስጥ ወጣሁ…በጠንካራ ግፊት ወደ ኋላ ጎትተሸ ልትመልሺኝ እየሞከርሽ ነው። ››
" እርግጠኛ ነኝ የአባትህን ጥፋት ማንም በአንተ ላይ ለማላከክ አይደፍርም ።"
‹‹እንደዛ ይመስልሻል? በራስሽ ሲደርስ በቅርብ ትረጂዋለሽ… ምክንያቱም አንቺን ከሰሎሜ ጋር ማወዳደር ይጀምራሉ."
"ያ አያስጨንቀኝም። ንጽጽሮችን እቀበላለሁ።"
"እርግጠኛ ነሽ?"
" ማለት?"
"እናትሽ ..ቅድስት አልነበረችም."
" እኔም ትሆናለች ብዬ ጠብቄ አላውቅም."
"ምናባዊ እናት በራስሽ አእምሮ ውስጥ የፈጠርሽ ይመስለኛል እና ሰሎሜ ያንን ክፍተት እንድትሞላልሽ እየጠበቅሽ ነው."
"ይህ አስቂኝ ነው….ግን እንዳስጠነቀቅኩሽ አስታውሺ" አለ በለሆሳስ።ትንፋሽ ወሰደና ንግግሩን ቀጠለ "ወደ አዲስ አበባሽ ተመለሺ፣ በዲዛይነር የተሰሩ ቅንጡ ልብሶችህን እና መግለጫዎችሽን የሆኑትን አጭር ቀሚስ እየለበሽ ዘና በይ። ያለፈውን ትተሽ ሂጂ፡፡ እዚህ ያለ ማንም ሰው በሰሎሜ ላይ የተፈጠረውን ያለፈውን ጊዜ ታሪክ ማስታወስ አይፈልግም… በዚህ ጊቢ በረት ውስጥ የሞተችው ሰሎሜ እንደሞተች በሰላም ብንተዋት ይሻላል"አላት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤32👍28
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
አለም በረጅሙ ተነፈሰችና "እናቴ እዚህ አካበቢ ነው የተገደለችው አይደል?"
"ትክክል እዚህ ነው የሞተችው" ብሎ በቁጣ መለሰላ፡፡
"የት? የትኛው ጋጣ አካባቢ?"
ዝም አላት…
‹‹ኩማንደር ሬሳዋን የት እንዳገኘህ አሳየኝ” ስትል ተማፀነችው፡፡
በረድፍ ካሉት የፈረስ ጋጣዎች ሁለተኛ ጋጣ ላይ ወሰዳትና። "እዚህ ነው የሞተችው"ብሎ ነገራት፡፡
አለም ሙሉ በሙሉ ደንዝዛ ቆመች፣ ከዚያም ወደ ገመዶ እስክትቀርብ ድረስ በዝግታ ወደፊት ሄደች። ወደ ጋጣው ዞረች። በውስጡ ምንም ፈረስ ሆነ ድርቆሽ አልነበረም, ወለል የተሸፈነው በጎማ ብቻ ነው. በሩ ተወግዷል ..ክፍት ነበር"ያ አደጋ ከተፈጠረ ጀምሮ በዚህ ጋጣ ውስጥ ፈረስ ገብቶበት አያውቅም?።"ስትል ጠየቀችው፡፡
በንቀት፣ "ጋሽ ፍሰሀ ስሜታዊ ስለሆነ ይሄን ውሳኔ ወስኗል›› አላት።
አለም በደም የተጨማለቀ አስከሬን በጋጣው ውስጥ እንደተጋደመ በምናቧ አሰበችና ..ተንቀጠቀጠች፡፡ ጠያቂ አይኖቿን ወደ ገመዶ አነሳች።ቆዳው በጉንጩ አጥንቶቹ ላይ በደንብ የተለጠጠ ይመስላል፣ ፡፡
ወንጀሉን የተፈጸመበትን ቦታ መጎብኘት ያሰበችውን ያህል ቀላል አልነበረም።"ስለ ጉዳዩ በዝርዝር ንገረኝ እባክህ?››አለችው፡፡
እያመነታ፣
“በጎኗ ተኝታ ነበር፣ ጭንቅላቷ በዚያ ጥግ ላይ ነበር፣ እግሮቿ እዚህ ነበሩ” እያለ በዝርዝር አስረዳት፡፡ባደረገው ቦቲ ጫፍ አንድ ቦታ እየነካ፡፡" በደም ተሸፍና ነበር፤ፀጉሯ በደም ተነክሮ ነበር… በሁሉም ቦታ ላይ ደም ነበር."
"ስንት ሰአት ነበር?" ብላ ጠየቀች።
" ሳገኛት?"
‹‹አዎ››
"ንጋት ላይ ነበረ. 12 ሰዓት ከሰላሳ አካባቢ."
"በዚያ ቀን አንተ እዚህ ምን ታደርግ ነበር?"
"ብዙውን ጊዜ ወደቢሮ ከመሄዴ በፊት ወደእዚህ መጥቼ ፈረሶቼን አይቼና ምግብ እንደተሰጣቸው አረጋግጬ ነበር የምሄደው››
"ሌሊቱን ሙሉ ቤትህ ነበርክ ?"
"ተጨማሪ መልስ ከፈለግሽ ፣ ጉዳዩን ለፍርድ ቤት በኩል አቅርቢው።" "እንደዛ አቅጃለሁ."
ወደ ኃላዋ ዞረችና ወደፊት ተንቀሳቀሰች…ከኃላ ተጠጋት፣ ክንዷን ይዞ ወደ እሱ አስጠጋት። ከባድ እና ጠንካራ ወንድ ነው። "ወ.ሪት አለም" በብስጭት እና ትዕግስት በማጣት አጉረመረመ
"ብልህ ነሽ… ይህን ጉዳይ ተይው። ካላደረግሽው ግን አንድ አካል ሊጎዳ ይችላል።"
"ማለት?"
ሰውነቱን ወደ እሷ ይበልጥ አቀረበ።‹‹ ሴትን የመግደል አቅም ነበረው?›› ስትል እራሷን ጠየቀች…በአጠቃላይ ለሴቶች ዝቅተኛ አመለካከት ያለው ይመስላል፤ነገር ግን እንደ ጁኒየር ሁሉ እሱም ሰሎሜን ይወዳት ነበር. እሷም በአንድ ወቅት እሱን ማግባት ትፈልግ ነበር። ምናልባት ገመዶን ጨምሮ ሁሉም ሰው ሰሎሜ ጎበና የተባለ ሌላ ሰው አግብታ እሷን እስክትፀንስ ድረስ እንደሚጋቡ ያስብ ይሆናል።አለም ገመዶ በማንኛውም ሁኔታ ሰሎሜን ሊገድላት እንደሚችል ማመን አልፈለገችም፤ነገር ግን እሱ ጨካኝ፣ ትዕቢተኛ፣እንደሆነም መካድም አልቻለችም ። ገዳይ ግን?አይመስልም። ወይም እሷ ሁልጊዜም ለፈርጣማ ሰውነትና ጥቋቁር ሰርሳሪ አይኖቹ ላላቸው ወንዶች ደካማ ስሜት ስላላት ይሆናል።
‹‹እናቴን ማን እንደገደላት እና ለምን እንደገደላት እስካውቅ ድረስ ይህን ምርመራ የማቋረጥ ሀሳብ የለኝም። የእናቴን ገዳይ ለማወቅ ህይወቴን በሙሉ ጠብቄአለሁ። አሁን እዚህ ደርሼ ተስፋ አልቆርጥም"
አለም ከጋጣው በወጣችበት ደቂቃ ኩማንደሩ የእርግማን መአቱን አዥጎደጎደ ።ከቀናት በፊት በአቶ ፍሰሀ ከስራው የተባረረው ሙስጠፋ በአቅራቢያው በሚገኝ ጋጣ ውስጥ ተደብቆ የሚያወሩትን ሁሉ ሰምቷቸው ነበር። በቦታው የተገኘው በአጋጣሚ እንጂ ንግግራቸውን ለማዳመጥ አስቦ አልነበረም። ብቸኝነት ስለተሰማውና ግራ ስለተጋባ ነበር በጨለማ ውስጥ ጭብጥብጥ ብሎ ሲተክዝ የነበረው… ከስራ ስላባረረው የቀድሞ አሠሪው እያሰላሰለ እንዴት ቂሙን እንደሚወጣ ማሰብ ብቻ ነበር የሚፈልገው። አሁን ግን በአጋጣሚ ያላሰበውን የኩማንደሩን እና የአለምን ውይይት ቃል በቃል ሰምቷል፡፡ እና የሰማው ነገር ደግሞ ለእሱ ልክ ከሰማይ እንደወረደ መና ነው የቆጠረው ፣ እሷ በደንብ የሚያውቃት የሰሎሜ ሴት ልጅ መሆኗን አውቋል፣ እዚህ የተገኘችው የእናቷን ግድያ ለመመርመር እንደሆነ በመስማቱ ተደንቋል። አቶ ፍሰሀ ላይ በቀሉን ለመወጣት ወርቃማ እድል እንዳገኘ ተሰምቷታል እና ያ የማይረባ ልጁንም ደህና አድርጎ ያጠፋዋል። ወደ ሠላሳ ዓመታት ጉልበቱን አንጠፍጥፎ አገልግሎት ነበር።ደህና፣ በመጨረሻ እድል ለሙስጠፋ ፈገግ እንዳለችለት ገባው ፡፡እሱ በትክክል ካርዶቹን መጫወት ከቻለ በመጨረሻ የተወሰነ ገንዘብ ሊያገኝ እንደሚችል አሰበ፡፡ የአሁኑ አዲሷ ሚስቱ ገንዘብ ስለሌለው እያመነጫጨቀችው ነው…እንደውም ከቤቷ ገፍትራ ወደበረንዳ ልትጥለው ቋፍ ላይ እንደሆነች ተረድቷል….ታዲያ በዚህ ሚስጥር የሆነ ገንዘብ ማግኘት ከቻለ ሀሳቧን እንደሚያስቀይራት እርግጠኛ ነው፡፡
ኩማንደሩ ስራውን ጨርሶ ጋጣውን ለቆ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ በትዕግሥት ማጣት ባለበት ተወሽቆ ነበር ያሳለፈው።ሙስጠፋ ትኩስ ገለባ ውስጥ የተጠቀጠቀበት ጋጥ ከመውጣቱ በፊት በአካባቢው ሌላ ሰው እንደሌለ ለማረጋገጥ ብዙ ጊዜ ጠብቋል።ከዛ ቀጥታ በጥላ ከተሸፈነው ኮሪደር ወርዶ አካባቢውን ለቆ ወደከተማ ሔደና ሁለት መለኪያ አረቄ ጠጥቶ ራሱን ካበረታታ በኃላ ስልኳን ለማግኘት ምን ማድረግ እንዳለበት ማሰብ ጀመረ….ግን በከተማ ውስጥ እሷን የሚያውቁ ሰዎች በቁጥር ስለነበሩ ቀላል ስራ አልነበረም….እንምንም በሁለተኛው ቀን ማግኘት ቻለና በኤርገንዶ ስልኩ ደወለላት…፡፡ ከአምስት ጥሪ በኃላ ስልኩ ተነሳ፡፡
"ወ.ሪት አለም ነሽ?"
"አዎ ማን ልበል?"
"ማወቅ አያስፈልገሽም ..እኔ አውቅሻለሁ እና ያ በቂ ነው።"
ግራ መበጋባት‹‹አልገባኝም ?" አለችው፡፡
"ስለ እናትሽ ግድያ ሁሉንም አውቃለሁ።"
ሙስጠፋ በድንገት ዝምታ ውስጥ በመግባቷ እየተደሰተ ..እስክታገግም ጠበቃት፡፡ ለእሷ ሚያደነዝ አይነት ድብዳ ዜና ነው የሆነባት፡፡
‹‹እየሰማሁ ነው።››አለችው፡፡
‹‹አሁን ማውራት አልችልም.፡፡"
‹‹ለምን አይሆንም?"
‹‹ስለማልችል ነው ..ጉዳዩ አደገኛ መሆኑን የምታውቂ መሰለኝ።››
በስልክ ከእሷ ጋር ለመግባት አደገኛ እንደሆነ አስቦል… አንድ ሰው ሰምቷት ለአቶ ፍሰሀ ወይም ለኩማንደሩ ሹክ ሊላቸው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አለው፡፡
‹‹መልሼ እደውልልሻለሁ።"አላት፡፡
‹‹ግን "
‹‹መልሼ እደውልልሻለሁ አልኩሽ እኮ…ስልኬን ጠብቂ…ደህና ሁኚ።››
ሙስጠፋ እሷ በምትገደልበት ጊዜ በቦታው ነበር.. እርሱ ጣልቃ ሳይገባ በተደበቀበት ሆኖ ሲመለከት ነበር ።ያንን ምሽት እንደ ትላንትናው የሆነውን ሁሉ ያስታወሰ። ይህን ሁሉ ጊዜ በሚስጥር ነበር ያያዘው። አሁን ግን የሚያወራበት ጊዜ መድረሱን አውቋል ። እናም ስለ ጉዳዩ ሁሉ ለዐቃቤት ሕጓ ለመናገር እስከ ሞት ድረስ ክፍያ ሊያስከፍለው እንደሚችል ያምናል…ግን ደግሞ ጥሩ ገንዘብም ሊያገኝበት የሚችልበት እድልም ሰፊ ነው፡።
/////
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
///
አለም በረጅሙ ተነፈሰችና "እናቴ እዚህ አካበቢ ነው የተገደለችው አይደል?"
"ትክክል እዚህ ነው የሞተችው" ብሎ በቁጣ መለሰላ፡፡
"የት? የትኛው ጋጣ አካባቢ?"
ዝም አላት…
‹‹ኩማንደር ሬሳዋን የት እንዳገኘህ አሳየኝ” ስትል ተማፀነችው፡፡
በረድፍ ካሉት የፈረስ ጋጣዎች ሁለተኛ ጋጣ ላይ ወሰዳትና። "እዚህ ነው የሞተችው"ብሎ ነገራት፡፡
አለም ሙሉ በሙሉ ደንዝዛ ቆመች፣ ከዚያም ወደ ገመዶ እስክትቀርብ ድረስ በዝግታ ወደፊት ሄደች። ወደ ጋጣው ዞረች። በውስጡ ምንም ፈረስ ሆነ ድርቆሽ አልነበረም, ወለል የተሸፈነው በጎማ ብቻ ነው. በሩ ተወግዷል ..ክፍት ነበር"ያ አደጋ ከተፈጠረ ጀምሮ በዚህ ጋጣ ውስጥ ፈረስ ገብቶበት አያውቅም?።"ስትል ጠየቀችው፡፡
በንቀት፣ "ጋሽ ፍሰሀ ስሜታዊ ስለሆነ ይሄን ውሳኔ ወስኗል›› አላት።
አለም በደም የተጨማለቀ አስከሬን በጋጣው ውስጥ እንደተጋደመ በምናቧ አሰበችና ..ተንቀጠቀጠች፡፡ ጠያቂ አይኖቿን ወደ ገመዶ አነሳች።ቆዳው በጉንጩ አጥንቶቹ ላይ በደንብ የተለጠጠ ይመስላል፣ ፡፡
ወንጀሉን የተፈጸመበትን ቦታ መጎብኘት ያሰበችውን ያህል ቀላል አልነበረም።"ስለ ጉዳዩ በዝርዝር ንገረኝ እባክህ?››አለችው፡፡
እያመነታ፣
“በጎኗ ተኝታ ነበር፣ ጭንቅላቷ በዚያ ጥግ ላይ ነበር፣ እግሮቿ እዚህ ነበሩ” እያለ በዝርዝር አስረዳት፡፡ባደረገው ቦቲ ጫፍ አንድ ቦታ እየነካ፡፡" በደም ተሸፍና ነበር፤ፀጉሯ በደም ተነክሮ ነበር… በሁሉም ቦታ ላይ ደም ነበር."
"ስንት ሰአት ነበር?" ብላ ጠየቀች።
" ሳገኛት?"
‹‹አዎ››
"ንጋት ላይ ነበረ. 12 ሰዓት ከሰላሳ አካባቢ."
"በዚያ ቀን አንተ እዚህ ምን ታደርግ ነበር?"
"ብዙውን ጊዜ ወደቢሮ ከመሄዴ በፊት ወደእዚህ መጥቼ ፈረሶቼን አይቼና ምግብ እንደተሰጣቸው አረጋግጬ ነበር የምሄደው››
"ሌሊቱን ሙሉ ቤትህ ነበርክ ?"
"ተጨማሪ መልስ ከፈለግሽ ፣ ጉዳዩን ለፍርድ ቤት በኩል አቅርቢው።" "እንደዛ አቅጃለሁ."
ወደ ኃላዋ ዞረችና ወደፊት ተንቀሳቀሰች…ከኃላ ተጠጋት፣ ክንዷን ይዞ ወደ እሱ አስጠጋት። ከባድ እና ጠንካራ ወንድ ነው። "ወ.ሪት አለም" በብስጭት እና ትዕግስት በማጣት አጉረመረመ
"ብልህ ነሽ… ይህን ጉዳይ ተይው። ካላደረግሽው ግን አንድ አካል ሊጎዳ ይችላል።"
"ማለት?"
ሰውነቱን ወደ እሷ ይበልጥ አቀረበ።‹‹ ሴትን የመግደል አቅም ነበረው?›› ስትል እራሷን ጠየቀች…በአጠቃላይ ለሴቶች ዝቅተኛ አመለካከት ያለው ይመስላል፤ነገር ግን እንደ ጁኒየር ሁሉ እሱም ሰሎሜን ይወዳት ነበር. እሷም በአንድ ወቅት እሱን ማግባት ትፈልግ ነበር። ምናልባት ገመዶን ጨምሮ ሁሉም ሰው ሰሎሜ ጎበና የተባለ ሌላ ሰው አግብታ እሷን እስክትፀንስ ድረስ እንደሚጋቡ ያስብ ይሆናል።አለም ገመዶ በማንኛውም ሁኔታ ሰሎሜን ሊገድላት እንደሚችል ማመን አልፈለገችም፤ነገር ግን እሱ ጨካኝ፣ ትዕቢተኛ፣እንደሆነም መካድም አልቻለችም ። ገዳይ ግን?አይመስልም። ወይም እሷ ሁልጊዜም ለፈርጣማ ሰውነትና ጥቋቁር ሰርሳሪ አይኖቹ ላላቸው ወንዶች ደካማ ስሜት ስላላት ይሆናል።
‹‹እናቴን ማን እንደገደላት እና ለምን እንደገደላት እስካውቅ ድረስ ይህን ምርመራ የማቋረጥ ሀሳብ የለኝም። የእናቴን ገዳይ ለማወቅ ህይወቴን በሙሉ ጠብቄአለሁ። አሁን እዚህ ደርሼ ተስፋ አልቆርጥም"
አለም ከጋጣው በወጣችበት ደቂቃ ኩማንደሩ የእርግማን መአቱን አዥጎደጎደ ።ከቀናት በፊት በአቶ ፍሰሀ ከስራው የተባረረው ሙስጠፋ በአቅራቢያው በሚገኝ ጋጣ ውስጥ ተደብቆ የሚያወሩትን ሁሉ ሰምቷቸው ነበር። በቦታው የተገኘው በአጋጣሚ እንጂ ንግግራቸውን ለማዳመጥ አስቦ አልነበረም። ብቸኝነት ስለተሰማውና ግራ ስለተጋባ ነበር በጨለማ ውስጥ ጭብጥብጥ ብሎ ሲተክዝ የነበረው… ከስራ ስላባረረው የቀድሞ አሠሪው እያሰላሰለ እንዴት ቂሙን እንደሚወጣ ማሰብ ብቻ ነበር የሚፈልገው። አሁን ግን በአጋጣሚ ያላሰበውን የኩማንደሩን እና የአለምን ውይይት ቃል በቃል ሰምቷል፡፡ እና የሰማው ነገር ደግሞ ለእሱ ልክ ከሰማይ እንደወረደ መና ነው የቆጠረው ፣ እሷ በደንብ የሚያውቃት የሰሎሜ ሴት ልጅ መሆኗን አውቋል፣ እዚህ የተገኘችው የእናቷን ግድያ ለመመርመር እንደሆነ በመስማቱ ተደንቋል። አቶ ፍሰሀ ላይ በቀሉን ለመወጣት ወርቃማ እድል እንዳገኘ ተሰምቷታል እና ያ የማይረባ ልጁንም ደህና አድርጎ ያጠፋዋል። ወደ ሠላሳ ዓመታት ጉልበቱን አንጠፍጥፎ አገልግሎት ነበር።ደህና፣ በመጨረሻ እድል ለሙስጠፋ ፈገግ እንዳለችለት ገባው ፡፡እሱ በትክክል ካርዶቹን መጫወት ከቻለ በመጨረሻ የተወሰነ ገንዘብ ሊያገኝ እንደሚችል አሰበ፡፡ የአሁኑ አዲሷ ሚስቱ ገንዘብ ስለሌለው እያመነጫጨቀችው ነው…እንደውም ከቤቷ ገፍትራ ወደበረንዳ ልትጥለው ቋፍ ላይ እንደሆነች ተረድቷል….ታዲያ በዚህ ሚስጥር የሆነ ገንዘብ ማግኘት ከቻለ ሀሳቧን እንደሚያስቀይራት እርግጠኛ ነው፡፡
ኩማንደሩ ስራውን ጨርሶ ጋጣውን ለቆ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ በትዕግሥት ማጣት ባለበት ተወሽቆ ነበር ያሳለፈው።ሙስጠፋ ትኩስ ገለባ ውስጥ የተጠቀጠቀበት ጋጥ ከመውጣቱ በፊት በአካባቢው ሌላ ሰው እንደሌለ ለማረጋገጥ ብዙ ጊዜ ጠብቋል።ከዛ ቀጥታ በጥላ ከተሸፈነው ኮሪደር ወርዶ አካባቢውን ለቆ ወደከተማ ሔደና ሁለት መለኪያ አረቄ ጠጥቶ ራሱን ካበረታታ በኃላ ስልኳን ለማግኘት ምን ማድረግ እንዳለበት ማሰብ ጀመረ….ግን በከተማ ውስጥ እሷን የሚያውቁ ሰዎች በቁጥር ስለነበሩ ቀላል ስራ አልነበረም….እንምንም በሁለተኛው ቀን ማግኘት ቻለና በኤርገንዶ ስልኩ ደወለላት…፡፡ ከአምስት ጥሪ በኃላ ስልኩ ተነሳ፡፡
"ወ.ሪት አለም ነሽ?"
"አዎ ማን ልበል?"
"ማወቅ አያስፈልገሽም ..እኔ አውቅሻለሁ እና ያ በቂ ነው።"
ግራ መበጋባት‹‹አልገባኝም ?" አለችው፡፡
"ስለ እናትሽ ግድያ ሁሉንም አውቃለሁ።"
ሙስጠፋ በድንገት ዝምታ ውስጥ በመግባቷ እየተደሰተ ..እስክታገግም ጠበቃት፡፡ ለእሷ ሚያደነዝ አይነት ድብዳ ዜና ነው የሆነባት፡፡
‹‹እየሰማሁ ነው።››አለችው፡፡
‹‹አሁን ማውራት አልችልም.፡፡"
‹‹ለምን አይሆንም?"
‹‹ስለማልችል ነው ..ጉዳዩ አደገኛ መሆኑን የምታውቂ መሰለኝ።››
በስልክ ከእሷ ጋር ለመግባት አደገኛ እንደሆነ አስቦል… አንድ ሰው ሰምቷት ለአቶ ፍሰሀ ወይም ለኩማንደሩ ሹክ ሊላቸው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አለው፡፡
‹‹መልሼ እደውልልሻለሁ።"አላት፡፡
‹‹ግን "
‹‹መልሼ እደውልልሻለሁ አልኩሽ እኮ…ስልኬን ጠብቂ…ደህና ሁኚ።››
ሙስጠፋ እሷ በምትገደልበት ጊዜ በቦታው ነበር.. እርሱ ጣልቃ ሳይገባ በተደበቀበት ሆኖ ሲመለከት ነበር ።ያንን ምሽት እንደ ትላንትናው የሆነውን ሁሉ ያስታወሰ። ይህን ሁሉ ጊዜ በሚስጥር ነበር ያያዘው። አሁን ግን የሚያወራበት ጊዜ መድረሱን አውቋል ። እናም ስለ ጉዳዩ ሁሉ ለዐቃቤት ሕጓ ለመናገር እስከ ሞት ድረስ ክፍያ ሊያስከፍለው እንደሚችል ያምናል…ግን ደግሞ ጥሩ ገንዘብም ሊያገኝበት የሚችልበት እድልም ሰፊ ነው፡።
/////
❤44👍5
አለም መኪናዋ አቁማ ወረደችና ዘጋችው። ከፍተኛ መረበሽ ውስጥ ነው ያለችው፡፡ ።ዛሬ በተቀበለችው ያልተጠበቀ የስልክ ጥሪ ምክንያት የምትይዘው የምትጨብጠውን አጥታለች። ምናልባት ጥሪው ስትጸልይለት የነበረ ትክክለኛው የዓይን እማኝ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን የአጭበርባሪ ሰውም ሊሆን ይችላል።እውነተኛ የአይን እማኝ ሆኖ ኩማንደር ገመዶ የእናትሽ ገዳይ ነው ብሎ ቢነግራት አሳዛኝ እንደሚሆንባት ታውቃለች።
አዲሱ ቢሮዋ ቁጭ ብላ ፊቷ የተቆለሉትን የስራ ፋይሎች አፍጥጣ እያየች በሀሳብ ሰምጣለች፡፡
እስካሁን ድረስ ያለው ጉዞው የግብር ከፋዮችን ገንዘብ ማባከን ብቻ ነው የሆነባት
፡፡እስካሁን የተማረችው ነገር ቢኖር ሦስቱ ሰዎች ሰሎሜን የአምልኮ ያህል ይወዷት እንደነበረ እና ይህም እሷን ለመግደል እንደ ጠንካራ መነሻ ሰበብ አድርጋ ልትወስደው እንደማትችል ነው ።ይህንን የሚያረጋግጥ ግን ምንም አይነት መረጃ አልነበራትም ቢሆንም ግን ትክክለኛ ተጠርጣሪ ሆኖ የቀረበው ገመዶ እናቷን እንዳልገደለ እርግጠኛ ነበረች፣ ነገር ግን ማን እንዳደረገው ለማወቅ ገና ምንም ፍንጭ የላትም።አለም ከፍሰሀ፣ ከጁኒየር እና ከገመዶ ጋር ብቻዋን አሳለፈ ኑዛዜያቸውን ተራ በተራ ከተቀበለቻቸው በኃላ እንደተአምር የሚታይ መረጃ እንደምታገኝ እርግጠኛ ነበረች። መጸጸት እና ንስሐ ከስብዕና መገለጫዎቻቸው ጋር አይጣጣምም። አንዱ በሌላው ላይ አይመሰክርም። ታማኝነታቸው በጠንካራ መሰረት ላይ የታነፀ ነው ፣ ምንም እንኳን ጓደኝነታቸው ከዚህ በፊት እንደነበረው ባይሆንም በራሱ ፍንጭ ነበር። የሰሎሜ መሞት እርስ በርስ እንዲተሳሰሩ አድርጓቸዋል?በድንገት የደወለላት ሰው ትክክለኛ የአይን እማኝ እንደሆነ አሁንም ተስፋ አድርጋለች። ከአሁን አሁን ይደውልልኛል ብላ ስጠብቅ ነበር፣ ይህም ሰውዬው እየቀለደባት መሆኑን የሚያሳይ ጠንካራ ማስረጃ ነው።
ሀሳቡ አለምን አሳመማት። ግንባሯን በእጆቿ መዳፍ ደግፋ አይኖቿን ጨፈነች። ይህን ለማድረግ የሚያስችል ጥንካሬ ነበራት?እሷ አማራጮችን ለመጠቀም ሞክራ ነበር፣ ግን ባዶ እጇን ነበር የመጣች። ማስረጃ ያስፈልጋት ነበር, ፡፡ሃሳቧን ከመቀየሯ በፊት ማብራቱን አጥፍታ ከቢሮ ወጣች። ሊፍትን ተወችና ደረጃውን ተጠቅማ ወደ ዳኛ ዋልልኝ ቢሮ መራመድ ጀመረች፣ለምሳ ከመውጣታቸው በፊት ልትደርስባቸው በማሰብ ደረጃውን በሩጫ ወጣች።ድንገት በአእምሮዋ ብልጭ ያለላትን ሀሳብ እስከነገ ማቆየት አትፈልግም።
በውሳኔዋ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ጊዜ እና እድል ነበራት። በሁለተኛው ፎቅ ላይ ያሉት ኮሪደሮች ባዶ ነበሩ። ዳኞች የእለቱን ስራቸውን ጨርሰው ቢሮቸውን ለቀው ወጥተዋል፡፡ እስከ ነገ ድረስ አይመለሱም።ወደምትፈልገው ዳኛ ቢሮ ስትሄድ እግሯ ጫማ ከወለሉ ጋር ሲላተም ሚያሰማው ቀጭ ቋ ድምፅ በአካባቢው በግልፅ ይሰማ ነበር፡፡ ፀሐፊው ፊት ለፊት ቆመች….በዚህ ሰዓት ባለጉዳይ በማየቷ ፀሀፊዋ ደስተኛ እንዳልሆነች በፊቷ መጨማደድ በግልፅ ያስታውቅባታል፡፡አለም ግድ አልነበራትም፡፡
ደረጃዎችን በፍጥነት በመወጣቷ የተነሳ በሚቆራረጥ ትንፋሿ
"በአፋጣኝ ከዳኛው ጋር መነጋገር አለብኝ።›› አለቻት፡፡
"ለእለቱን ስራ አጠናቆ ሊወጣ ነው"
"ጉዳዩ በጣም አስፈላጊ እና አጣዳፊ ነው፣ እንደዛ ባይሆን አላስቸግረውም ነበር።››
ፀሀፊዋ አለምን አቁማ ወደዳኛው ቢሮ ተራማዳ በራፉን በጥንቃቄ አንኳኳች እና ወደውስጥ ገባች…ብዙ ሳተቆይ ተመልሳ ወጣችና ወደአለም ቀርባ …በአጭሩ
‹‹ሊያይሽ ተስማምቷል ››አለቻት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
አዲሱ ቢሮዋ ቁጭ ብላ ፊቷ የተቆለሉትን የስራ ፋይሎች አፍጥጣ እያየች በሀሳብ ሰምጣለች፡፡
እስካሁን ድረስ ያለው ጉዞው የግብር ከፋዮችን ገንዘብ ማባከን ብቻ ነው የሆነባት
፡፡እስካሁን የተማረችው ነገር ቢኖር ሦስቱ ሰዎች ሰሎሜን የአምልኮ ያህል ይወዷት እንደነበረ እና ይህም እሷን ለመግደል እንደ ጠንካራ መነሻ ሰበብ አድርጋ ልትወስደው እንደማትችል ነው ።ይህንን የሚያረጋግጥ ግን ምንም አይነት መረጃ አልነበራትም ቢሆንም ግን ትክክለኛ ተጠርጣሪ ሆኖ የቀረበው ገመዶ እናቷን እንዳልገደለ እርግጠኛ ነበረች፣ ነገር ግን ማን እንዳደረገው ለማወቅ ገና ምንም ፍንጭ የላትም።አለም ከፍሰሀ፣ ከጁኒየር እና ከገመዶ ጋር ብቻዋን አሳለፈ ኑዛዜያቸውን ተራ በተራ ከተቀበለቻቸው በኃላ እንደተአምር የሚታይ መረጃ እንደምታገኝ እርግጠኛ ነበረች። መጸጸት እና ንስሐ ከስብዕና መገለጫዎቻቸው ጋር አይጣጣምም። አንዱ በሌላው ላይ አይመሰክርም። ታማኝነታቸው በጠንካራ መሰረት ላይ የታነፀ ነው ፣ ምንም እንኳን ጓደኝነታቸው ከዚህ በፊት እንደነበረው ባይሆንም በራሱ ፍንጭ ነበር። የሰሎሜ መሞት እርስ በርስ እንዲተሳሰሩ አድርጓቸዋል?በድንገት የደወለላት ሰው ትክክለኛ የአይን እማኝ እንደሆነ አሁንም ተስፋ አድርጋለች። ከአሁን አሁን ይደውልልኛል ብላ ስጠብቅ ነበር፣ ይህም ሰውዬው እየቀለደባት መሆኑን የሚያሳይ ጠንካራ ማስረጃ ነው።
ሀሳቡ አለምን አሳመማት። ግንባሯን በእጆቿ መዳፍ ደግፋ አይኖቿን ጨፈነች። ይህን ለማድረግ የሚያስችል ጥንካሬ ነበራት?እሷ አማራጮችን ለመጠቀም ሞክራ ነበር፣ ግን ባዶ እጇን ነበር የመጣች። ማስረጃ ያስፈልጋት ነበር, ፡፡ሃሳቧን ከመቀየሯ በፊት ማብራቱን አጥፍታ ከቢሮ ወጣች። ሊፍትን ተወችና ደረጃውን ተጠቅማ ወደ ዳኛ ዋልልኝ ቢሮ መራመድ ጀመረች፣ለምሳ ከመውጣታቸው በፊት ልትደርስባቸው በማሰብ ደረጃውን በሩጫ ወጣች።ድንገት በአእምሮዋ ብልጭ ያለላትን ሀሳብ እስከነገ ማቆየት አትፈልግም።
በውሳኔዋ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ጊዜ እና እድል ነበራት። በሁለተኛው ፎቅ ላይ ያሉት ኮሪደሮች ባዶ ነበሩ። ዳኞች የእለቱን ስራቸውን ጨርሰው ቢሮቸውን ለቀው ወጥተዋል፡፡ እስከ ነገ ድረስ አይመለሱም።ወደምትፈልገው ዳኛ ቢሮ ስትሄድ እግሯ ጫማ ከወለሉ ጋር ሲላተም ሚያሰማው ቀጭ ቋ ድምፅ በአካባቢው በግልፅ ይሰማ ነበር፡፡ ፀሐፊው ፊት ለፊት ቆመች….በዚህ ሰዓት ባለጉዳይ በማየቷ ፀሀፊዋ ደስተኛ እንዳልሆነች በፊቷ መጨማደድ በግልፅ ያስታውቅባታል፡፡አለም ግድ አልነበራትም፡፡
ደረጃዎችን በፍጥነት በመወጣቷ የተነሳ በሚቆራረጥ ትንፋሿ
"በአፋጣኝ ከዳኛው ጋር መነጋገር አለብኝ።›› አለቻት፡፡
"ለእለቱን ስራ አጠናቆ ሊወጣ ነው"
"ጉዳዩ በጣም አስፈላጊ እና አጣዳፊ ነው፣ እንደዛ ባይሆን አላስቸግረውም ነበር።››
ፀሀፊዋ አለምን አቁማ ወደዳኛው ቢሮ ተራማዳ በራፉን በጥንቃቄ አንኳኳች እና ወደውስጥ ገባች…ብዙ ሳተቆይ ተመልሳ ወጣችና ወደአለም ቀርባ …በአጭሩ
‹‹ሊያይሽ ተስማምቷል ››አለቻት፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤35👍7👎1
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
ፀሀፊዋ አለምን አቁማ ወደዳኛው ቢሮ ተራማዳ በራፉን በጥንቃቄ አንኳኳች እና ወደውስጥ ገባች…ብዙ ሳተቆይ ተመልሳ ወጣችና ወደአለም ቀርባ …በአጭሩ
‹‹ሊያይሽ ተስማምቷል ››አለቻት፡፡
"አመሰግናለሁ።" አለችና እሷን አልፋ ወደ ክፍሉ ገባች።
"ወ.ሮ አለም …በዚህ ጊዜ ስለምንድነው የምታናግሪኝ?" ዳኛ ዋልልኝ ኮቱን ከመስቀያው ላይ እየጎተተ ነበር የሚያናግራት። "ያለ ቀጠሮ ሰው ቢሮ የመግባት መጥፎ ልማድ ያለሽ ይመስላል። እንደምታየው እኔ ልወጣ ነው። ልጄ ስርጉት ያለ እኔ እራት መብላት አትወድም እና እሷን ማስጠበቅ ለእኔ አሳፋሪ ነው።"
"ሁለታችሁንም ይቅርታ እጠይቃለሁ ክቡር ዳኛ… ለፀሀፊዎ እንደነገርኩት ጉዳዬ በጣም አስቸኳይ ስለሆነብኝ ነው ።"
"እሺ…ልስማው?"
"መቀመጥ እንችላለን?"
" ቆሜ መስማት እችላለሁ …ምን ልትነግሪኝ ፈልገሽ ነው?"
"የእናቴ አስከሬን ተቆፍሮ እንዲወጣ እና ዳግም የፎረንስክ ምርመራ እንዲደረግበት የፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዲሰጡልኝ እፈልጋለሁ."
ዳኛው ቀስ ብሎ ወንበሩ ላይ ተቀመጠ። አለም ግልፅ የሆነ ጭንቀት ተመለከተችበት።
"ይቅርታ፣ ምን አልሺኝ?፧"
"ክቡር ዳኛ ያልኩትን እንደሰሙኝ አምናለሁ፣ ግን ጥያቄዬን መድገም አስፈላጊ ከሆነ፣ አደርገዋለሁ።"
ዳኛው እጁን አወዛወዘ። "አይ. ቸሩ ጌታ አይሆንም. አንድ ጊዜ መስማት በቂ ነው…ለምን እንዲህ አይነት አስቀያሚ ነገር ማድረግ ፈለግሽ?"
"የመፈለግ ጉዳይ ሳይሆን ግድ ሆኖብኝ ነው, በጣም አስፈላጊ ነው ብዬ ባላምን ኖሮ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ አልጠይቅም ነበር."
"አስቲ ተቀመጪና… ምክንያቶችሽን አስረጂኝ።››
"እናቴ ላይ ወንጀል ተፈጽሟል ፣ነገር ግን ትክክለኛው ፍርድ ተገኝቷል ብዬ አላምንም ።"
"እንደዛ ማድረግ አትችዬም " ብሎ ጮኸ።
"አልሰማሽም።ከአመታት በኃላ ድንገት ከመሀከላችን ተገኘሽ፣ ወዲያው መሠረተ ቢስ ውንጀላ ይዘሽ ትረብሺኝ ያዝሽ፣ ለበቀል ቆርጠሻል።"
"ይህ እውነት አይደለም" ስትል ለመከላከል ሞከረች ፡፡ " ለመሆኑ ሀለቃሽ ግርማ ስለዚህ ጉዳይ ምን ይላል?"
"አሱ ለጊዜው የለም ..ለጥቂት ቀናት እረፍት ወሰዶ ወደ አዲስአበባ የሄደ ይመስኛል።›› ዳኛው ተናደደ።
" ለማንኛውም ጥያቄሽ … ጥሩ ሀሳብ አይመስለኝም››
" ክቡር ዳኛ ማስረጃ እንድፈልግ ይፈቅዱልኛል?"
"ምንም ማስረጃ አታገኚም" ሲል አፅንዖት ተናገረ፡፡
"ከእናቴ አስከሬን የተወሰነ መነሻ ሚሆነን መረጃ ልናገኝ እንችላለን."
" የተገደለችውና ሬሳዋ የተገኘው እኮ ከዛሬ ከሃያ አምስት ዓመታት በፊት ነበር ።"
"በዚያን ጊዜ ለሬሳ ምርመራ ለማድረግ ቴክኖሎጂዎች አልነበሩም… ..በአሁኑ ጊዜ ግን ነገሮች የተለዩ ናቸው፡፡እኔ በግሌ ጎበዝ የተባለ የፎረንሲክ ስፔሻሊስት አውቃለሁ።አሁን ለሚከሰቱ የወንጀል ድርጊቶች በተደጋጋሚ ጊዜ ከእሱ ጋር የመስራት እድል ነበረኝ …እሱና ጎደኞቹ በጣም ውጤታማ ናቸው ..በዛን ወቅት ባለው ቴክኖሎጂ ሊገኝ ያልቻለ የሆነ ነገር ሊያገኝልን እንደሚችል ዋስትና እሰጥዎታለሁ።››
"ጥያቄሽን እንደጥያቄ እወስደዋለሁ።››
"መልሱ ለዛሬ ማታ ቢደርስልኝ ምስጋናዬ ከፍ ያለ ነው ።"
" ይቅርታ ወ/ሪት አለም ማድረግ የምችለው በአንድ ጀምበር አስብበት እና በጠዋት መልሱን እሰጥሻለው።እስከዛው ሀሳብሽን ለውጠሽ ጥያቄውን እንደምትሰርዢ ተስፋ አደርጋለሁ።"
"አላደርገውም።››
ዳኛው ከተቀመጠበት ተነሳ። "ደክሞኛል፣ በዛ ላይ ርቦኛል፣ እናም በዚህ የማይመች ቦታ ላይ ስላስቀመጥሺኝ ተበሳጫችቻለሁ።" የክስ አመልካች ጣት አነጣጥሮባት። "እኔ እንደህ አይነት የተጨመላለቀ ነገር አልወድም."አላት፡፡
" ይህ በጣም አስፈላጊ ባይሆን እኔም አላደርገውም ነበር."
"አስፈላጊ አይደለም."
"እኔ ደግሞ እንደሆነ አምናለሁ" ስትል በግትርነት መለሰች።
" አሁን፣ በቂ ጊዜዬን ወስደሻል። ይሄኔ ልጄ ስርጉት ተጨንቃለች።››
‹‹ ደህና ይሁኑ ብላ ።"ከክፍሉ ወጣች።
///
አለም ቀጥታ ወደመኪናዋ አመራችና ወደቤቷ ነው የነዳችው… መንገድ በትራፊክ ስለተጨናነቀ ወደቤቷ ለመመለስ ረጅም ጊዜ ነበር የወሰደባት፡፡
ክፍሏ ገብታ አልጋዋ ላይ ተዘርራ ትንሽ እረፍት ለመውሰድ ሞከረች…ከዛ ተነሳች….ማስታወሻዎቿን እንደገና ለመገምገም ሞከረች….ወዲያው ሰለቻት፡፡ ቴሌቪዥኑን ለመክፈት ወሰነች። ሪሞቷን አነሳችና ከፈተች፡፡ፊልም ላይ አደረገችውና ሰውነቷን ለመለቃለቅ ልብሷን አወላልቃ ወደሻወር ቤት ሄደችና መታጠብ ጀመረች……ታጥባ ከመጨረሷ በፊት አንድ ሰው በሯን ሲያንኳኳ ሰማች… እርጥብ ፀጉሯን በፎጣ ጠቅልላለች። ረጅምና ነጭ ካባዋን አደረገችና እና ወገቧ ላይ ያለውን መቀነት ለማሰር እያስተካከለች ወደሳሎን ሄደችና በበራፉ ቀዳዳ በማጮለቅ ማንነቱን ለማረጋገጥ ሞከረች፡፡
የሰንሰለት መቆለፊያው እስከሚፈቅደው ድረስ በሩን ከፈተችው "እንኳን ደህና መጣህ ኩማንደር ምነው በሰላም?"
ኮስተር ብሎ"በሩን ክፈቺ" አላት
"ለምን?"
" ካንቺ ጋር መነጋገር አለብኝ።"
"ስለ ምን?"
‹‹ወደ ውስጥ ካስገባሺኝ እነግርሻለሁ።
አለም አልተንቀሳቀሰችም."በሩን ልክፈት ወይስ ምን?"እለች ከራሷ ጋር ሙግት ገባች፡፡ግድግዳ ላይ የተንጠለጠለውን ሰዓት ተመለከተች….ለሶስት እሩብ ጉዳይ ይላል፡፡
"እዚያው ሆነህ ላናግርህ እችላለሁ።"
"በሩን ክፈቺ" ብሎ ጮኸ።
‹‹ሰውነቴን እየታጠብኩ ነበር."አለም ሰንሰለቱን አላቀቀችና በሩን ከፍታ ወደ ጎን ቆመች።
"አንድ ሰው እየጠበቅሽ ነበር?"
"አይደለም."
ኮፍያውን ከጭንቅላቱ አወለቀና ጠረጴዛው ላይ አስቀምጦ … ወደ ወንበር ሄዶ ተቀመጠ እና ወደ ቴሌቭዥን ስክሪን ተመለከተ፣ ልብስ ያልለበሱ ጥንዶች ተቆላልፈው ይሳሳማሉ ። ካሜራው የወንዱ ከንፈር ከሴቷ ጡት ጋር ሲጣበቅ እያሳየ ነው፡፡
"ስለአቋረጥኩሽ መናደድሽ አይገርምም።››አላት ሪሞቱን አነሳችና አጠፋችው "አያየሁት አልነበር."
"በራፍሽን ለሚያንኳኳ ሰው ሁል ጊዜ በርሽን ትከፍቺያለሽ?"
"በዚህ ከተማ ውስጥ ከፍተኛው የህግ አስከባሪ የፖሊስ መኮንን ነህ። አንተን ማመን ካልቻልኩ ማንን ማመን እችላለሁ?ይልቅ በዚህ ማታ ለምን መጣህ? እስከ ጠዋት ድረስ መጠበቅ አልቻልክም?"
"ዳኛ ዋልልኝ ደውሎልኝ ስለጠየቅሽው የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ነገረኝ.››
በንዴት ሲመታ የነበረው ልቧ በፍጥነት ቀዘቀዘ፣ "በዚህ ከተማ ውስጥ የግል የሚባል ነገር የለም ማለት ነው?"ብላ ጠየቀች፡፡
"ብዙ አይደለም"
"በከተማው ክልል ውስጥ ያለ ማንኛውም ሰው የእናንተ ቡድን ሳይፈቅድለት ማስነጠስ የሚችል አይመስለኝም።"
"እንደፈለግሽ ተርጉሚው …አንቺ ዙሪያችን እየተሸከረከርሽ ጉድጓዳችንን ስትቆፍሪ ምን እንድናደርግ ጠብቀሽ ነበር?"
"የእናቴን መቃብር እንዲከፈት ማድረግ ትክክለኛ የግድያዋን መንሴ ለማወቅ ወሳኝ እርምጃ ነው ብዬ ባላስብ ኖሮ የምረበሻት ይመስላችኋል?" ሞቅ ባለ ስሜት ጠየቀች ።
‹‹አንቺ ቋሚንም ሆን ሟችን ከመረበሽ ውጭ ምን ስራ አለሽ?››
"አምላኬ ሆይ ጥያቄውን ማቅረብ እንኳን ቀላል ብሎኝ ያደረኩት ይመስልሃል? እና ዳኛው ከ አንተ እና ከሰዎች ሁሉ ጋር መማከር ለምን አስፈለገው?"
‹‹ለምን ብለሽ ትጠይቂያለሽ እንዴ?… ተጠርጣሪ ስለሆንኩ ነዋ?"
"ዳኛው በዚህ ጉዳይ ከአንተ ጋር መወያየቱ ሞያዊ ሥነ ምግባር የጎደለው ሽማግሌ መሆኑን ነው የሚያሳየው "
"እኔ እኮ የከተማው ፖሊስ አዛዥ ነኝ፣ አስታውሺ?"
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
፡
፡
///
ፀሀፊዋ አለምን አቁማ ወደዳኛው ቢሮ ተራማዳ በራፉን በጥንቃቄ አንኳኳች እና ወደውስጥ ገባች…ብዙ ሳተቆይ ተመልሳ ወጣችና ወደአለም ቀርባ …በአጭሩ
‹‹ሊያይሽ ተስማምቷል ››አለቻት፡፡
"አመሰግናለሁ።" አለችና እሷን አልፋ ወደ ክፍሉ ገባች።
"ወ.ሮ አለም …በዚህ ጊዜ ስለምንድነው የምታናግሪኝ?" ዳኛ ዋልልኝ ኮቱን ከመስቀያው ላይ እየጎተተ ነበር የሚያናግራት። "ያለ ቀጠሮ ሰው ቢሮ የመግባት መጥፎ ልማድ ያለሽ ይመስላል። እንደምታየው እኔ ልወጣ ነው። ልጄ ስርጉት ያለ እኔ እራት መብላት አትወድም እና እሷን ማስጠበቅ ለእኔ አሳፋሪ ነው።"
"ሁለታችሁንም ይቅርታ እጠይቃለሁ ክቡር ዳኛ… ለፀሀፊዎ እንደነገርኩት ጉዳዬ በጣም አስቸኳይ ስለሆነብኝ ነው ።"
"እሺ…ልስማው?"
"መቀመጥ እንችላለን?"
" ቆሜ መስማት እችላለሁ …ምን ልትነግሪኝ ፈልገሽ ነው?"
"የእናቴ አስከሬን ተቆፍሮ እንዲወጣ እና ዳግም የፎረንስክ ምርመራ እንዲደረግበት የፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዲሰጡልኝ እፈልጋለሁ."
ዳኛው ቀስ ብሎ ወንበሩ ላይ ተቀመጠ። አለም ግልፅ የሆነ ጭንቀት ተመለከተችበት።
"ይቅርታ፣ ምን አልሺኝ?፧"
"ክቡር ዳኛ ያልኩትን እንደሰሙኝ አምናለሁ፣ ግን ጥያቄዬን መድገም አስፈላጊ ከሆነ፣ አደርገዋለሁ።"
ዳኛው እጁን አወዛወዘ። "አይ. ቸሩ ጌታ አይሆንም. አንድ ጊዜ መስማት በቂ ነው…ለምን እንዲህ አይነት አስቀያሚ ነገር ማድረግ ፈለግሽ?"
"የመፈለግ ጉዳይ ሳይሆን ግድ ሆኖብኝ ነው, በጣም አስፈላጊ ነው ብዬ ባላምን ኖሮ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ አልጠይቅም ነበር."
"አስቲ ተቀመጪና… ምክንያቶችሽን አስረጂኝ።››
"እናቴ ላይ ወንጀል ተፈጽሟል ፣ነገር ግን ትክክለኛው ፍርድ ተገኝቷል ብዬ አላምንም ።"
"እንደዛ ማድረግ አትችዬም " ብሎ ጮኸ።
"አልሰማሽም።ከአመታት በኃላ ድንገት ከመሀከላችን ተገኘሽ፣ ወዲያው መሠረተ ቢስ ውንጀላ ይዘሽ ትረብሺኝ ያዝሽ፣ ለበቀል ቆርጠሻል።"
"ይህ እውነት አይደለም" ስትል ለመከላከል ሞከረች ፡፡ " ለመሆኑ ሀለቃሽ ግርማ ስለዚህ ጉዳይ ምን ይላል?"
"አሱ ለጊዜው የለም ..ለጥቂት ቀናት እረፍት ወሰዶ ወደ አዲስአበባ የሄደ ይመስኛል።›› ዳኛው ተናደደ።
" ለማንኛውም ጥያቄሽ … ጥሩ ሀሳብ አይመስለኝም››
" ክቡር ዳኛ ማስረጃ እንድፈልግ ይፈቅዱልኛል?"
"ምንም ማስረጃ አታገኚም" ሲል አፅንዖት ተናገረ፡፡
"ከእናቴ አስከሬን የተወሰነ መነሻ ሚሆነን መረጃ ልናገኝ እንችላለን."
" የተገደለችውና ሬሳዋ የተገኘው እኮ ከዛሬ ከሃያ አምስት ዓመታት በፊት ነበር ።"
"በዚያን ጊዜ ለሬሳ ምርመራ ለማድረግ ቴክኖሎጂዎች አልነበሩም… ..በአሁኑ ጊዜ ግን ነገሮች የተለዩ ናቸው፡፡እኔ በግሌ ጎበዝ የተባለ የፎረንሲክ ስፔሻሊስት አውቃለሁ።አሁን ለሚከሰቱ የወንጀል ድርጊቶች በተደጋጋሚ ጊዜ ከእሱ ጋር የመስራት እድል ነበረኝ …እሱና ጎደኞቹ በጣም ውጤታማ ናቸው ..በዛን ወቅት ባለው ቴክኖሎጂ ሊገኝ ያልቻለ የሆነ ነገር ሊያገኝልን እንደሚችል ዋስትና እሰጥዎታለሁ።››
"ጥያቄሽን እንደጥያቄ እወስደዋለሁ።››
"መልሱ ለዛሬ ማታ ቢደርስልኝ ምስጋናዬ ከፍ ያለ ነው ።"
" ይቅርታ ወ/ሪት አለም ማድረግ የምችለው በአንድ ጀምበር አስብበት እና በጠዋት መልሱን እሰጥሻለው።እስከዛው ሀሳብሽን ለውጠሽ ጥያቄውን እንደምትሰርዢ ተስፋ አደርጋለሁ።"
"አላደርገውም።››
ዳኛው ከተቀመጠበት ተነሳ። "ደክሞኛል፣ በዛ ላይ ርቦኛል፣ እናም በዚህ የማይመች ቦታ ላይ ስላስቀመጥሺኝ ተበሳጫችቻለሁ።" የክስ አመልካች ጣት አነጣጥሮባት። "እኔ እንደህ አይነት የተጨመላለቀ ነገር አልወድም."አላት፡፡
" ይህ በጣም አስፈላጊ ባይሆን እኔም አላደርገውም ነበር."
"አስፈላጊ አይደለም."
"እኔ ደግሞ እንደሆነ አምናለሁ" ስትል በግትርነት መለሰች።
" አሁን፣ በቂ ጊዜዬን ወስደሻል። ይሄኔ ልጄ ስርጉት ተጨንቃለች።››
‹‹ ደህና ይሁኑ ብላ ።"ከክፍሉ ወጣች።
///
አለም ቀጥታ ወደመኪናዋ አመራችና ወደቤቷ ነው የነዳችው… መንገድ በትራፊክ ስለተጨናነቀ ወደቤቷ ለመመለስ ረጅም ጊዜ ነበር የወሰደባት፡፡
ክፍሏ ገብታ አልጋዋ ላይ ተዘርራ ትንሽ እረፍት ለመውሰድ ሞከረች…ከዛ ተነሳች….ማስታወሻዎቿን እንደገና ለመገምገም ሞከረች….ወዲያው ሰለቻት፡፡ ቴሌቪዥኑን ለመክፈት ወሰነች። ሪሞቷን አነሳችና ከፈተች፡፡ፊልም ላይ አደረገችውና ሰውነቷን ለመለቃለቅ ልብሷን አወላልቃ ወደሻወር ቤት ሄደችና መታጠብ ጀመረች……ታጥባ ከመጨረሷ በፊት አንድ ሰው በሯን ሲያንኳኳ ሰማች… እርጥብ ፀጉሯን በፎጣ ጠቅልላለች። ረጅምና ነጭ ካባዋን አደረገችና እና ወገቧ ላይ ያለውን መቀነት ለማሰር እያስተካከለች ወደሳሎን ሄደችና በበራፉ ቀዳዳ በማጮለቅ ማንነቱን ለማረጋገጥ ሞከረች፡፡
የሰንሰለት መቆለፊያው እስከሚፈቅደው ድረስ በሩን ከፈተችው "እንኳን ደህና መጣህ ኩማንደር ምነው በሰላም?"
ኮስተር ብሎ"በሩን ክፈቺ" አላት
"ለምን?"
" ካንቺ ጋር መነጋገር አለብኝ።"
"ስለ ምን?"
‹‹ወደ ውስጥ ካስገባሺኝ እነግርሻለሁ።
አለም አልተንቀሳቀሰችም."በሩን ልክፈት ወይስ ምን?"እለች ከራሷ ጋር ሙግት ገባች፡፡ግድግዳ ላይ የተንጠለጠለውን ሰዓት ተመለከተች….ለሶስት እሩብ ጉዳይ ይላል፡፡
"እዚያው ሆነህ ላናግርህ እችላለሁ።"
"በሩን ክፈቺ" ብሎ ጮኸ።
‹‹ሰውነቴን እየታጠብኩ ነበር."አለም ሰንሰለቱን አላቀቀችና በሩን ከፍታ ወደ ጎን ቆመች።
"አንድ ሰው እየጠበቅሽ ነበር?"
"አይደለም."
ኮፍያውን ከጭንቅላቱ አወለቀና ጠረጴዛው ላይ አስቀምጦ … ወደ ወንበር ሄዶ ተቀመጠ እና ወደ ቴሌቭዥን ስክሪን ተመለከተ፣ ልብስ ያልለበሱ ጥንዶች ተቆላልፈው ይሳሳማሉ ። ካሜራው የወንዱ ከንፈር ከሴቷ ጡት ጋር ሲጣበቅ እያሳየ ነው፡፡
"ስለአቋረጥኩሽ መናደድሽ አይገርምም።››አላት ሪሞቱን አነሳችና አጠፋችው "አያየሁት አልነበር."
"በራፍሽን ለሚያንኳኳ ሰው ሁል ጊዜ በርሽን ትከፍቺያለሽ?"
"በዚህ ከተማ ውስጥ ከፍተኛው የህግ አስከባሪ የፖሊስ መኮንን ነህ። አንተን ማመን ካልቻልኩ ማንን ማመን እችላለሁ?ይልቅ በዚህ ማታ ለምን መጣህ? እስከ ጠዋት ድረስ መጠበቅ አልቻልክም?"
"ዳኛ ዋልልኝ ደውሎልኝ ስለጠየቅሽው የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ነገረኝ.››
በንዴት ሲመታ የነበረው ልቧ በፍጥነት ቀዘቀዘ፣ "በዚህ ከተማ ውስጥ የግል የሚባል ነገር የለም ማለት ነው?"ብላ ጠየቀች፡፡
"ብዙ አይደለም"
"በከተማው ክልል ውስጥ ያለ ማንኛውም ሰው የእናንተ ቡድን ሳይፈቅድለት ማስነጠስ የሚችል አይመስለኝም።"
"እንደፈለግሽ ተርጉሚው …አንቺ ዙሪያችን እየተሸከረከርሽ ጉድጓዳችንን ስትቆፍሪ ምን እንድናደርግ ጠብቀሽ ነበር?"
"የእናቴን መቃብር እንዲከፈት ማድረግ ትክክለኛ የግድያዋን መንሴ ለማወቅ ወሳኝ እርምጃ ነው ብዬ ባላስብ ኖሮ የምረበሻት ይመስላችኋል?" ሞቅ ባለ ስሜት ጠየቀች ።
‹‹አንቺ ቋሚንም ሆን ሟችን ከመረበሽ ውጭ ምን ስራ አለሽ?››
"አምላኬ ሆይ ጥያቄውን ማቅረብ እንኳን ቀላል ብሎኝ ያደረኩት ይመስልሃል? እና ዳኛው ከ አንተ እና ከሰዎች ሁሉ ጋር መማከር ለምን አስፈለገው?"
‹‹ለምን ብለሽ ትጠይቂያለሽ እንዴ?… ተጠርጣሪ ስለሆንኩ ነዋ?"
"ዳኛው በዚህ ጉዳይ ከአንተ ጋር መወያየቱ ሞያዊ ሥነ ምግባር የጎደለው ሽማግሌ መሆኑን ነው የሚያሳየው "
"እኔ እኮ የከተማው ፖሊስ አዛዥ ነኝ፣ አስታውሺ?"
❤39👍4
‹‹እሱን መቼም አልረሳውም። ያ አሁንም ዳኛው ከጀርባዬ ሆኖ ካንተ ጋር እንዲዶልትብኝ ሰበብ ሊሆን አይችልም… ለምን የአስከሬኑን መውጣት እንዲህ ፈራው? የፎረንሲክ ምርመራው ያጋልጥብኛል ብሎ የሰጋው የደበቀው ወንጀል አለ እንዴ ?››
‹‹ያቀረብሽው ጥያቄ ችግር ገጥሞታል።››
"ምን አይነት ችግር…. ያ የሬሳ ሣጥን የታሸገው ማንን ለመጠበቅ ነው?››
"አንቺን።"
"እኔን?"
"አዎ ፣የሰሎሜ አስከሬን ከመቃብር ሊወጣ አይችልም…. ተቃጥሏል"
‹‹ምን?››የሰማችውን ነገር ማመን አልቻለችም፡፡አፏን መረራት፡፡
‹‹አዎ ..ሞታ አስከሬኗ ለምርመራ ወደሆስፒታል ከተወሰደ በኃላ ድንገት ባልታወቀ ምክንያት በሆስፒታሉ እሳት ተነስቶ ስለነበረ የሬሳ ማስቀመጫ ክፍሉን ጨምሮ የተወሰኑ የሆስፒታሉ ክፍሎች ወድመው ነበር….እና የእናትሽም ሬሳ ተቃጥሏል …ለመታሰቢያ እንዲሆን እንዲሁ ከቃጠሎ አመድ ወስደን ነው በሳጥን አድርገኝ የቀበርነው፡፡››
‹‹ቢያንስ አጥንቷ አልተገኘም ነበር?፡፡››
‹‹የተወሰኑ አጥንቶች ተገኝተው ነበር..ግን በወቅቱ ከስምንት በላይ ሬሳ ነበረ..የትኛው አጥንት የማንኛው እንደሆነ በዛን ዘመን ለመለየት በጣም አስቸጋሪ ስለነበረ…እንደዛ ማድረግ አልቻልንም››
ለተወሰኑ ደቂቃዎች ደንዝዛ ዝም አለች….ከዛ ድንገት እንደመባነን አለችና‹አሁን ይበልጥ እያመንኩ መጣሁ››ስትል ተናገረች፡፡
‹‹ማለት? ምኑን ነው ያመንሽው?››
‹‹የእናቴ ገዳይ አሁንም ተገቢውን ቅጣት እንዳላገኘ..እና እሱን ከቅጣት ለማዳን ሆስፒታል እስከማቃጠል ድረስ የሚያደርስ ጭካኔ ያለው ደጋፊ ቡድን መኖሩን››
‹‹አእምሮሽ ግን እንዴት ነው የሚሰራው….?››
‹‹በትክክል ነዋ….እናቴ ሬሳ ሆስፒታል በገባበት ቅፅበት እሳት መነሳቱ ያጋጣሚ ነው ብለህ እንዳታስቀኝ..ደግሞስ ይሄንን ጉዳይ አያቴ እንዴት ሳትነግረኝ….?.››
‹‹እኔ እንጃ…ለምን እንዳልነገረችሽ እሷኑ መጠየቅ ነው…ምን አልባት ገምት ካልሺኝ ግን ይሄንን ነገሮችን ባልተገባ መንገድ የመፈትፈት ፀባይሽን ስለምታውቅ ይመስለኛል፡፡››
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹ያቀረብሽው ጥያቄ ችግር ገጥሞታል።››
"ምን አይነት ችግር…. ያ የሬሳ ሣጥን የታሸገው ማንን ለመጠበቅ ነው?››
"አንቺን።"
"እኔን?"
"አዎ ፣የሰሎሜ አስከሬን ከመቃብር ሊወጣ አይችልም…. ተቃጥሏል"
‹‹ምን?››የሰማችውን ነገር ማመን አልቻለችም፡፡አፏን መረራት፡፡
‹‹አዎ ..ሞታ አስከሬኗ ለምርመራ ወደሆስፒታል ከተወሰደ በኃላ ድንገት ባልታወቀ ምክንያት በሆስፒታሉ እሳት ተነስቶ ስለነበረ የሬሳ ማስቀመጫ ክፍሉን ጨምሮ የተወሰኑ የሆስፒታሉ ክፍሎች ወድመው ነበር….እና የእናትሽም ሬሳ ተቃጥሏል …ለመታሰቢያ እንዲሆን እንዲሁ ከቃጠሎ አመድ ወስደን ነው በሳጥን አድርገኝ የቀበርነው፡፡››
‹‹ቢያንስ አጥንቷ አልተገኘም ነበር?፡፡››
‹‹የተወሰኑ አጥንቶች ተገኝተው ነበር..ግን በወቅቱ ከስምንት በላይ ሬሳ ነበረ..የትኛው አጥንት የማንኛው እንደሆነ በዛን ዘመን ለመለየት በጣም አስቸጋሪ ስለነበረ…እንደዛ ማድረግ አልቻልንም››
ለተወሰኑ ደቂቃዎች ደንዝዛ ዝም አለች….ከዛ ድንገት እንደመባነን አለችና‹አሁን ይበልጥ እያመንኩ መጣሁ››ስትል ተናገረች፡፡
‹‹ማለት? ምኑን ነው ያመንሽው?››
‹‹የእናቴ ገዳይ አሁንም ተገቢውን ቅጣት እንዳላገኘ..እና እሱን ከቅጣት ለማዳን ሆስፒታል እስከማቃጠል ድረስ የሚያደርስ ጭካኔ ያለው ደጋፊ ቡድን መኖሩን››
‹‹አእምሮሽ ግን እንዴት ነው የሚሰራው….?››
‹‹በትክክል ነዋ….እናቴ ሬሳ ሆስፒታል በገባበት ቅፅበት እሳት መነሳቱ ያጋጣሚ ነው ብለህ እንዳታስቀኝ..ደግሞስ ይሄንን ጉዳይ አያቴ እንዴት ሳትነግረኝ….?.››
‹‹እኔ እንጃ…ለምን እንዳልነገረችሽ እሷኑ መጠየቅ ነው…ምን አልባት ገምት ካልሺኝ ግን ይሄንን ነገሮችን ባልተገባ መንገድ የመፈትፈት ፀባይሽን ስለምታውቅ ይመስለኛል፡፡››
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍34❤12
#አሜን_በይ_አደራ
ያየሽ አይኑ ይጥፋ
እግርና እግሩን ያርግበት ወልካፋ።
ቡዳ እንደበላዉ ልጅ አይኑ ፈጦ ይቅር አንቺኑ ያየበት
አናቱ ቅል ይሁን አንቺን ያሰበበት
ልቡ ስራ ታቁም ካንቺ የከጀለበት።
ፍቅርሽ እስክመጣ
ፍቅር የተባለ ከወንድ መኖ ይዉጣ
ጠንጋራ ያድርገዉ አንቺን ሊያይ የመጣ።
በፈገግታ ማርኮ ቀልብሽን ለሻተ
ጥርሶቹን አግጥጦ ለተንከራተተ
መጋኛ አግኝቶልኝ ከንፈሩን ያጣመዉ
ጥርሶቹን አርግፎ በድዱ ያስቀረዉ።
እኔ ያንቺዉ መዉደድ ስቃይ እንዳይገባኝ
ቅናት እንዳይገባኝ
ፍርሀት እንዳይገባኝ
ችግር እንዳይገባኝ
የሀገሬዉ ተባዕት በርሀብ ይቀጣ
ሆዱን እያሰበ ወዳንቺ እንዳይመጣ።
የሚበላዉ ይጣ
የሚጠጣዉ ይጣ።
በቃላት ሊያጠምድሽ አንደበቱ ናፍቆ ስምሽን የጠራ
ያሰበዉም ቢሆን ከኔ ፍቅር ጋራ።
ሀረግ ሊደረድር ተፈጥሮ የሰራዉ
ጉሮሮ፣ትናጋ፣ምላስ ከከንፈሩ
ላንቃዉም ሳይቀሩ
የጨዉ ሀዉልት ሆነዉ እዛዉ ደርቀዉ ይቅሩ።
ብቻ ግን አደራ ይሄ ሁሉ ሲሆን
አንዱን አያሳይሽ እንዳይገባሽ ሀዘን
ሲከፋሽ አልወድም።
🔘ትዝታ ወልዴ 🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ያየሽ አይኑ ይጥፋ
እግርና እግሩን ያርግበት ወልካፋ።
ቡዳ እንደበላዉ ልጅ አይኑ ፈጦ ይቅር አንቺኑ ያየበት
አናቱ ቅል ይሁን አንቺን ያሰበበት
ልቡ ስራ ታቁም ካንቺ የከጀለበት።
ፍቅርሽ እስክመጣ
ፍቅር የተባለ ከወንድ መኖ ይዉጣ
ጠንጋራ ያድርገዉ አንቺን ሊያይ የመጣ።
በፈገግታ ማርኮ ቀልብሽን ለሻተ
ጥርሶቹን አግጥጦ ለተንከራተተ
መጋኛ አግኝቶልኝ ከንፈሩን ያጣመዉ
ጥርሶቹን አርግፎ በድዱ ያስቀረዉ።
እኔ ያንቺዉ መዉደድ ስቃይ እንዳይገባኝ
ቅናት እንዳይገባኝ
ፍርሀት እንዳይገባኝ
ችግር እንዳይገባኝ
የሀገሬዉ ተባዕት በርሀብ ይቀጣ
ሆዱን እያሰበ ወዳንቺ እንዳይመጣ።
የሚበላዉ ይጣ
የሚጠጣዉ ይጣ።
በቃላት ሊያጠምድሽ አንደበቱ ናፍቆ ስምሽን የጠራ
ያሰበዉም ቢሆን ከኔ ፍቅር ጋራ።
ሀረግ ሊደረድር ተፈጥሮ የሰራዉ
ጉሮሮ፣ትናጋ፣ምላስ ከከንፈሩ
ላንቃዉም ሳይቀሩ
የጨዉ ሀዉልት ሆነዉ እዛዉ ደርቀዉ ይቅሩ።
ብቻ ግን አደራ ይሄ ሁሉ ሲሆን
አንዱን አያሳይሽ እንዳይገባሽ ሀዘን
ሲከፋሽ አልወድም።
🔘ትዝታ ወልዴ 🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤5😁1
#ትናንትና_ማታ
ላሟሟሽ ሲገባኝ፣እንዳሞሌ አጥቤሽ
በመጨረስ ፋንታ
ለነገ ቆጥቤሽ
አስተርፌሽ ለሰው
የጸጸት ሱናሚ ፤ዓለሜን አመሰው፡፡
ምነው ቢቻል ኖሮ
ፈገግታሽን ቋጥሮ
ሙዳይ ውስጥ መደበቅ
ጃንደረባ ቀጥሮ
ጭንሽን ማስጠበቅ
ክፍት ልቤን ይዤ፤ ዝግ ደጅሽን ጠናሁ
በሰበብ ወድጄሽ ፤ያለሰበብ ቀናሁ፡፡
ፍቅር በተባለ፤ ግራ ገቢ ነገር
ከጨመተው አገር
ከሰከነው ቀየ
መናፍቅ ይመስል፤ ባዋጅ ተነጥየ
እንደካፖርቴ ቁልፍ፤ ልቤን የትም ጥየ
የትም ስከተልሽ
የትም ሆኖ እድልሽ፤
ሁሉ ያንች ወዳጅ
ሁሉ ባላንጣየ
መፈቀር ሆኖ ጣሽ፤ መቅናት ሆኖ ጣየ
ላንቺ ብስል ፍሬ፤ ለኔ ገለባ ግርድ
ላንቺ እቅፍ አበባ፤ ለኔ እቅፍ ሙሉ ብርድ
ማነው የበየነው ፣ይህን ግፈኛ ፍርድ፡፡
🔘በዕውቀቱ ሥዩም🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ላሟሟሽ ሲገባኝ፣እንዳሞሌ አጥቤሽ
በመጨረስ ፋንታ
ለነገ ቆጥቤሽ
አስተርፌሽ ለሰው
የጸጸት ሱናሚ ፤ዓለሜን አመሰው፡፡
ምነው ቢቻል ኖሮ
ፈገግታሽን ቋጥሮ
ሙዳይ ውስጥ መደበቅ
ጃንደረባ ቀጥሮ
ጭንሽን ማስጠበቅ
ክፍት ልቤን ይዤ፤ ዝግ ደጅሽን ጠናሁ
በሰበብ ወድጄሽ ፤ያለሰበብ ቀናሁ፡፡
ፍቅር በተባለ፤ ግራ ገቢ ነገር
ከጨመተው አገር
ከሰከነው ቀየ
መናፍቅ ይመስል፤ ባዋጅ ተነጥየ
እንደካፖርቴ ቁልፍ፤ ልቤን የትም ጥየ
የትም ስከተልሽ
የትም ሆኖ እድልሽ፤
ሁሉ ያንች ወዳጅ
ሁሉ ባላንጣየ
መፈቀር ሆኖ ጣሽ፤ መቅናት ሆኖ ጣየ
ላንቺ ብስል ፍሬ፤ ለኔ ገለባ ግርድ
ላንቺ እቅፍ አበባ፤ ለኔ እቅፍ ሙሉ ብርድ
ማነው የበየነው ፣ይህን ግፈኛ ፍርድ፡፡
🔘በዕውቀቱ ሥዩም🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤7😁1
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
ኩማደሩ በቤት ውስጥ ምርጥ የተባለ ውስኪ እያለው በአውራ ጎዳናው ላይ ወደሚገኝ ግርግር ወደሚበዛበት መጠጥ ቤት ገብቶ ለመጠጣት ለምን እንደመረጠ ማወቅ አልቻለም። ምናልባት አዕምሮው ስለተጨናነቀ የተጨናነቀ ቦታ ፈልጎ ሊሆን ይችላል…እሾህን በእሾህ ለማክሰም ።የቡና ቤት አስተናጋጅ መጠጥ እንዲያመጣለት በምልክት ነገረው።ውስኪውን ወደ ብርጭቆው ሲቀዳ እያየ"አመሰግናለሁ" አለ ብቻውን እየቆዘመ ውስኪውን መሳብ ጀመረ፡፡
የጠጣው ውስኪው ቀስ በቀስ በሆዱ ውስጥ እሳት እንዲንቀለቀል እያደረገ ነው። ሲጠጣ ጨጓራውን በጣም ያመዋል….በዛም ምክንያት እርግፍ አድርጎ ለማቆም ሁሌ ይወስናል
..ግን ደግሞ ምክንያት ፈልጎ መጠጣቱን አይተውም…ቢሆንም እስኪሰክር ጠጥቶ አያውቅም በፍጽም የአባቱን ስህተት መድገም አይፈልግም…።ይህ የሌሊቱ የመጨረሻ መጠጥ እንደሚሆን ወሰነ …አዘዘ ፡፡ገና ህጻን ሳለ ነው እንደአባቱ መሆን እንደሌለበት ወስኖ የነበር ።የወህኒ ቤት ወፍ ወይም መነኩሴ፣ የጠፈር ተመራማሪ ወይም የመቃብር ጉድጓድ ቆፋሪ፣ የእንስሳት ጠባቂ ወይም ትልቅ አዳኝ ሆኖ ሊያድግ ይችላል፣ ነገር ግን አንድ መሆን የማይፈልገው ነገር ሰካራም መሆን ብቻ ነበር። ቀድሞውኑ በቤተሰቡ ውስጥ አንዱ ፕሮፌሽናል ጠጪ ነበራቸው እና ያ ደግሞ በጣም በቂ እንደሆነ ያምናል፡፡
"ሂይ ኩማንደር " የሚል ንግግር ከሀሳቡ አናጠበው፡፡
አንገቱን ቀና ሲያደርግ የለበሰችው ጅንስ ሱሪ የጠበባት እና ፊቷን በሚካፕ ያደመቀች ውብ ሴት ፊት ለፊቱ ቆማለች፡፡ይህቺን ሴት ከረጅም ጊዜ በፊት ጀምሮ ያውቃታል….፡፡
‹‹ሰላም ሮዛ።››
"ቢራ ትጋዘኛለህ ብዬ በማመን ነው ከጓደኞቼ ተነጥዬ የመጣሁት?"አለችው በተቃራኒው ኮሪደር ጥግ ከላይ ተቀምጠው ቢራ እየጠጡ ወደ ሚሳሳቁ ሁለት ሴቶች እየጠቆመችው፡፡
"ይቻላል።" አለና እንድትቀመጥ ካደረጋት በኃላ ትዕዛዙን ወደ አስተናጋጁ አስተላለፈ። ትኩር ብላ እያየችው ነው…ብቻውን ከእሷ ጋር መቀመጡ ምቾት ስላልሰጠው..‹‹ከፈለግሽ ጓደኞችሽን ጥሪያቸው››አላት፣ ከአንድ ሴት ጋር ለብቻ ከመሆን ከሶስት ሴት ጋር መሆን የተሻለ መስሎ ስለተሰማው ነው ሶስት ሴቶችን ለመጋበዝ ፍቃደኛ የሆነው፡፡
"አይ እነሱ የሞቀ ጫወታ ይዘዋል …አታስቸግራቸው" አለችው በማሽኮርመም ፡፡
"እየተዝናናችሁ ነው?››
"አዎ..እኛ ሴቶችም አንዳንዴ ወጣ ማለት አያስፈልገንም ትላለህ ?"
"አይ ጥሩ ነው፡፡"
ያዘዘችው ቢራ መጣላትና እየተጎነጨች ማውራቷን ቀጠለች‹‹ከቤት ተያይዘን ስንወጣ ፊልም ቤት ለመግባት ነበር..ግን እንደአለመታደል ሆኖ ፊልሙ ያየነው ስለሆነ ሀሳባችንን ቀየርንና ወደእዚህ ጎራ አልን…እና ደግሞ ደስ የሚለው አንተን አገኘሁህ››
‹‹ጥሩ ነው››ብሎ በአጭሩ መለሰላት፡፡
ሮዛ በቀላሉ የምትተወው አይነት ሴት አልነበረችም። "አይ ኩማንደር ሁል ጊዜ በራስህ ዙሪያ የምትሽከረከር ብቸኛ ፍጡር ነህ።"የሚል አስተያየት ጣል አደረገችበት
" ብቸኝነት ምርጫዬ ነው."ሲል መለሰላት
"አውቃለሁ ግን አሁንም…" እጇን አንቀሳቀሰችና ታፋው አካባቢ አስቀመጠች…በድንጋጤ ግራና ቀኙን አየና..ቀስ ብሎ እጇን አንሸራቶ ነፃ ወጣ፡፡
"ምናልባት አንተን ማስደሰት እችል ይሆናል፡፡ " አለችው ፡፡ " እስቲ እናያለን››አላት፡፡
"ሰባተኛ ክፍል እያለሁ ጀምሮ በጣም ወድጄህ ነበር። መቼስ ያንን አታውቅም አይደል?"
"አይ ያንን አላውቅም ነበር."
"እሺ አሁን ነገርኩህ ። በወቅቱ አብዬት ፍሬ ትምህርት ቤት እየተማርን እያለ አፈቅርህ ነበር…..ግን ያኔ ተነጠቅኩ። የዚያች ልጅ ስም ማን ነበር? በእነ ጁኒዬር የከብቶች በረት ውስጥ የተገደለችው?"
"ሰሎሜ."
"አዎ. በእሷ ላይ ተመስጠህ ነበር አይደል? ወደሀይስኩል ስንገባም በግልፅ ፍቅረኛማቾች መሆናችሁን በይፋ አሳወጃችሁ…ከዚያም እኔም ተስፋ ቆርጬ አግብቼ ልጆች ወለድኩ." ለንግግሯ ፍላጎት እንደሌለው አላስተዋለችም።
"'በእርግጥ አሁን ባሌ ሞቷል፣ እና ልጆቼም እራሳቸውን ችለው ከቤት ወጥተዋል….አንተ ግን በዚ ሁሉ ዘመን ትራስ ታቅፈህ ታድራለህ…ነው ወይስ ሳልሰማ አገባህ?››
"አይመስለኝም።"
‹‹እስካሁን ››ወደ ፊት ቀረበችው፣
"ምናልባት እኔን እየጠበቅከኝ ይሆናል፡፡››ብላ ወንበሯን አንሸራታ ወደእሱ አቀረበችውና እላዩ ላይ ተለጠፈች፣እሱም ቀኝ እጁን ሰነዘረና"ጡቶቿን በእጁ እያሻሸ ምላሽ ሰጣት፡፡ የጡት ጫፎቿ በቲሸርትዋ ላይ ጠንካራ እና የተለየ ስሜት ፈጠሩበት። የሆነ ሆኖ፣ ግልጽነቷ ልክ እንደ አለም ንፁህ እና ባዶ ጣቶች ከነጭ ጋወን ውስጥ አጮልቆ እንደሚወጣ የሚያማልሉ አልነበረም።
በአለም ነጭ ካባ ስር ምን አለ? ብሎ እንዲያስብ ስለተገደደ አላስደሰተውም። ለምን ብሎ አሰበ።አለም በጣም ቆንጆ ነበረች. ከንፈሮቿ ተከፍለው እርጥብ ነበሩ። ሳይፈልግ ከአለም ከሜካፕ ነፃ ከሆኑ ከንፈሮች ጋር አነጻጽሯቸዋል፣ ነገር ግን አሁንም ሞቃት እና እርጥብ፣ የሚሳም እና ሴሰኛ፣እንደሆኑም እርግጠኛ ቢሆንም ምንም አይነት ሙከራ ሳያደርግ የቢራዋን ዋጋ የሚሸፍን ብር ከጂንስ ኪሱ ውስጥ በማውጣት ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠና
‹‹መሄድ አለብኝ"በማለት ከተቀመጠበት ተነሳ፡፡
"ግን እኔ ያሰብኩት…."
"ወደ ጓደኞችሽ ብትመለሺ ይሻላል፣ አለበለዚያ ፓርቲው ያመልጥሻል ።"አላት፡፡ ከጓደኞቾ ጋር በፊት ያልነበሩ አራት የሚሆኑ ወንዶች ተቀላለቅለዋቸው ሞቅ ያለ ቡድን መስርተው ነበር….፡፡
‹‹ሮዛ ስለየሁሽ ደስ ብሎኛል›› አለና ኩማንደር ኮፍያውን ዝቅ አድርጎ ፊቱን በከፈል ሸፈነና ወጥቶ ሄደ፣ ፡፡
እና ስለአለም መብሰልሰሉን ቀጠለ..ትናንት ማታ የእናቷ አስከሬን እንደተቃጠለ ሲነግራት ፊቷ ላይ የተመለከተው ሀዘን አሁንም ትዝ ይለዋል፡፡
"ዳኛ ዋልልኝ ያውቅ ነበር?" ስትል ጠየቀችው፡፡
"እነሆ እኔ የማውቀው ነገር ቢኖር እሱ ጠርቶኝ የፈለጋችሁት ነገር የማይቻል ነው ማለቱን ነው፣ "
"የእናቴ አስከሬን መቃጠሉን የሚያውቅ ከሆነ ለምን እራሱ አልነገረኝም?"
"የእኔ ግምት አንቺ ለዜናው የምታሳይውን ትዕይንት ማየት ስለማይፈልግ ይመስለኛል "
"አዎ" ብላ ትኩረቷን ሳትከፋፍል አጉረመረመች፣
"ሁከትን አይወድም። ››
በዝምታ ተመለከተችው። "ቆሻሻ ስራውን እንድትሰራለት ነው አይደል የላከህ ?። ››ነበር ያለችው፡፡
ኩማንደሩ አስተያየት ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆኑ ጓንቱን አንስቶ አጠለቀ…ኮፍያውንም መልሶ አደረገ ።
"አሁን ደንግጠሻል ..ግን አይዞሽ ደህና ትሆኚያለሽ?"
"ደህና ነኝ።"
"ጥሩ ››
ጥቋቁር አይኖቿ በእንባ ተሞሉ እና አፏ በትንሹ ተንቀጠቀጠ። ድንገት ወደእሱ ተንቀሳቀሰችና እጆቿን ከወገብዋ ጋር አጣበቀች..እና ተሸጎጠችበት። ያን አጥር እንደገና ከመገንባቷ በፊት፣ እጆቹን አንሸራትቶ ወደ እሱ ጎተታት። እሷ ሞቃት ትንፋሽ እና ጥሩ መዓዛ ነበራት በሀዘኗ ውስጥ ደካማ ሆናለች. እጆቿ ሳይጨነቁ ወደ ጎን ተንጠልጥለዋል።
"ኦ አምላኬ እባክህ በዚህ ፈተና ውስጥ እንዳልፍ አታድርገኝ" ስትል በሹክሹክታ ተናገረች እና ጡቶቿ ሲንቀጠቀጡ ተሰማት። እንባዋን ሲንጠባጠብ በልብሱ አልፎ እስኪሰማው ድረስ ጭንቅላቷን ወደ እሱ አስጠጋች። ፀጉሯን የጠቀለለችበት ፎጣ ተንሸራቶ መሬት ላይ ወደቀ። ፀጉሯ እርጥብ ነበር። በወቅቱ እሷን መሳም እንደሌለበት ለራሱ እየተናገረ ነው… ነገር ግን ከንፈሩ ፀጉሯን ከዚያም የአንገቷ ስር ሽታን ወደውስጡ እየማገ ስለሆነ እየደነዘዘ ነበር፡።በዚያን ጊዜ፣ ከባድ የፍትወት ስሜት አቅበጠበጠው፣ እናም በጣም
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
ኩማደሩ በቤት ውስጥ ምርጥ የተባለ ውስኪ እያለው በአውራ ጎዳናው ላይ ወደሚገኝ ግርግር ወደሚበዛበት መጠጥ ቤት ገብቶ ለመጠጣት ለምን እንደመረጠ ማወቅ አልቻለም። ምናልባት አዕምሮው ስለተጨናነቀ የተጨናነቀ ቦታ ፈልጎ ሊሆን ይችላል…እሾህን በእሾህ ለማክሰም ።የቡና ቤት አስተናጋጅ መጠጥ እንዲያመጣለት በምልክት ነገረው።ውስኪውን ወደ ብርጭቆው ሲቀዳ እያየ"አመሰግናለሁ" አለ ብቻውን እየቆዘመ ውስኪውን መሳብ ጀመረ፡፡
የጠጣው ውስኪው ቀስ በቀስ በሆዱ ውስጥ እሳት እንዲንቀለቀል እያደረገ ነው። ሲጠጣ ጨጓራውን በጣም ያመዋል….በዛም ምክንያት እርግፍ አድርጎ ለማቆም ሁሌ ይወስናል
..ግን ደግሞ ምክንያት ፈልጎ መጠጣቱን አይተውም…ቢሆንም እስኪሰክር ጠጥቶ አያውቅም በፍጽም የአባቱን ስህተት መድገም አይፈልግም…።ይህ የሌሊቱ የመጨረሻ መጠጥ እንደሚሆን ወሰነ …አዘዘ ፡፡ገና ህጻን ሳለ ነው እንደአባቱ መሆን እንደሌለበት ወስኖ የነበር ።የወህኒ ቤት ወፍ ወይም መነኩሴ፣ የጠፈር ተመራማሪ ወይም የመቃብር ጉድጓድ ቆፋሪ፣ የእንስሳት ጠባቂ ወይም ትልቅ አዳኝ ሆኖ ሊያድግ ይችላል፣ ነገር ግን አንድ መሆን የማይፈልገው ነገር ሰካራም መሆን ብቻ ነበር። ቀድሞውኑ በቤተሰቡ ውስጥ አንዱ ፕሮፌሽናል ጠጪ ነበራቸው እና ያ ደግሞ በጣም በቂ እንደሆነ ያምናል፡፡
"ሂይ ኩማንደር " የሚል ንግግር ከሀሳቡ አናጠበው፡፡
አንገቱን ቀና ሲያደርግ የለበሰችው ጅንስ ሱሪ የጠበባት እና ፊቷን በሚካፕ ያደመቀች ውብ ሴት ፊት ለፊቱ ቆማለች፡፡ይህቺን ሴት ከረጅም ጊዜ በፊት ጀምሮ ያውቃታል….፡፡
‹‹ሰላም ሮዛ።››
"ቢራ ትጋዘኛለህ ብዬ በማመን ነው ከጓደኞቼ ተነጥዬ የመጣሁት?"አለችው በተቃራኒው ኮሪደር ጥግ ከላይ ተቀምጠው ቢራ እየጠጡ ወደ ሚሳሳቁ ሁለት ሴቶች እየጠቆመችው፡፡
"ይቻላል።" አለና እንድትቀመጥ ካደረጋት በኃላ ትዕዛዙን ወደ አስተናጋጁ አስተላለፈ። ትኩር ብላ እያየችው ነው…ብቻውን ከእሷ ጋር መቀመጡ ምቾት ስላልሰጠው..‹‹ከፈለግሽ ጓደኞችሽን ጥሪያቸው››አላት፣ ከአንድ ሴት ጋር ለብቻ ከመሆን ከሶስት ሴት ጋር መሆን የተሻለ መስሎ ስለተሰማው ነው ሶስት ሴቶችን ለመጋበዝ ፍቃደኛ የሆነው፡፡
"አይ እነሱ የሞቀ ጫወታ ይዘዋል …አታስቸግራቸው" አለችው በማሽኮርመም ፡፡
"እየተዝናናችሁ ነው?››
"አዎ..እኛ ሴቶችም አንዳንዴ ወጣ ማለት አያስፈልገንም ትላለህ ?"
"አይ ጥሩ ነው፡፡"
ያዘዘችው ቢራ መጣላትና እየተጎነጨች ማውራቷን ቀጠለች‹‹ከቤት ተያይዘን ስንወጣ ፊልም ቤት ለመግባት ነበር..ግን እንደአለመታደል ሆኖ ፊልሙ ያየነው ስለሆነ ሀሳባችንን ቀየርንና ወደእዚህ ጎራ አልን…እና ደግሞ ደስ የሚለው አንተን አገኘሁህ››
‹‹ጥሩ ነው››ብሎ በአጭሩ መለሰላት፡፡
ሮዛ በቀላሉ የምትተወው አይነት ሴት አልነበረችም። "አይ ኩማንደር ሁል ጊዜ በራስህ ዙሪያ የምትሽከረከር ብቸኛ ፍጡር ነህ።"የሚል አስተያየት ጣል አደረገችበት
" ብቸኝነት ምርጫዬ ነው."ሲል መለሰላት
"አውቃለሁ ግን አሁንም…" እጇን አንቀሳቀሰችና ታፋው አካባቢ አስቀመጠች…በድንጋጤ ግራና ቀኙን አየና..ቀስ ብሎ እጇን አንሸራቶ ነፃ ወጣ፡፡
"ምናልባት አንተን ማስደሰት እችል ይሆናል፡፡ " አለችው ፡፡ " እስቲ እናያለን››አላት፡፡
"ሰባተኛ ክፍል እያለሁ ጀምሮ በጣም ወድጄህ ነበር። መቼስ ያንን አታውቅም አይደል?"
"አይ ያንን አላውቅም ነበር."
"እሺ አሁን ነገርኩህ ። በወቅቱ አብዬት ፍሬ ትምህርት ቤት እየተማርን እያለ አፈቅርህ ነበር…..ግን ያኔ ተነጠቅኩ። የዚያች ልጅ ስም ማን ነበር? በእነ ጁኒዬር የከብቶች በረት ውስጥ የተገደለችው?"
"ሰሎሜ."
"አዎ. በእሷ ላይ ተመስጠህ ነበር አይደል? ወደሀይስኩል ስንገባም በግልፅ ፍቅረኛማቾች መሆናችሁን በይፋ አሳወጃችሁ…ከዚያም እኔም ተስፋ ቆርጬ አግብቼ ልጆች ወለድኩ." ለንግግሯ ፍላጎት እንደሌለው አላስተዋለችም።
"'በእርግጥ አሁን ባሌ ሞቷል፣ እና ልጆቼም እራሳቸውን ችለው ከቤት ወጥተዋል….አንተ ግን በዚ ሁሉ ዘመን ትራስ ታቅፈህ ታድራለህ…ነው ወይስ ሳልሰማ አገባህ?››
"አይመስለኝም።"
‹‹እስካሁን ››ወደ ፊት ቀረበችው፣
"ምናልባት እኔን እየጠበቅከኝ ይሆናል፡፡››ብላ ወንበሯን አንሸራታ ወደእሱ አቀረበችውና እላዩ ላይ ተለጠፈች፣እሱም ቀኝ እጁን ሰነዘረና"ጡቶቿን በእጁ እያሻሸ ምላሽ ሰጣት፡፡ የጡት ጫፎቿ በቲሸርትዋ ላይ ጠንካራ እና የተለየ ስሜት ፈጠሩበት። የሆነ ሆኖ፣ ግልጽነቷ ልክ እንደ አለም ንፁህ እና ባዶ ጣቶች ከነጭ ጋወን ውስጥ አጮልቆ እንደሚወጣ የሚያማልሉ አልነበረም።
በአለም ነጭ ካባ ስር ምን አለ? ብሎ እንዲያስብ ስለተገደደ አላስደሰተውም። ለምን ብሎ አሰበ።አለም በጣም ቆንጆ ነበረች. ከንፈሮቿ ተከፍለው እርጥብ ነበሩ። ሳይፈልግ ከአለም ከሜካፕ ነፃ ከሆኑ ከንፈሮች ጋር አነጻጽሯቸዋል፣ ነገር ግን አሁንም ሞቃት እና እርጥብ፣ የሚሳም እና ሴሰኛ፣እንደሆኑም እርግጠኛ ቢሆንም ምንም አይነት ሙከራ ሳያደርግ የቢራዋን ዋጋ የሚሸፍን ብር ከጂንስ ኪሱ ውስጥ በማውጣት ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠና
‹‹መሄድ አለብኝ"በማለት ከተቀመጠበት ተነሳ፡፡
"ግን እኔ ያሰብኩት…."
"ወደ ጓደኞችሽ ብትመለሺ ይሻላል፣ አለበለዚያ ፓርቲው ያመልጥሻል ።"አላት፡፡ ከጓደኞቾ ጋር በፊት ያልነበሩ አራት የሚሆኑ ወንዶች ተቀላለቅለዋቸው ሞቅ ያለ ቡድን መስርተው ነበር….፡፡
‹‹ሮዛ ስለየሁሽ ደስ ብሎኛል›› አለና ኩማንደር ኮፍያውን ዝቅ አድርጎ ፊቱን በከፈል ሸፈነና ወጥቶ ሄደ፣ ፡፡
እና ስለአለም መብሰልሰሉን ቀጠለ..ትናንት ማታ የእናቷ አስከሬን እንደተቃጠለ ሲነግራት ፊቷ ላይ የተመለከተው ሀዘን አሁንም ትዝ ይለዋል፡፡
"ዳኛ ዋልልኝ ያውቅ ነበር?" ስትል ጠየቀችው፡፡
"እነሆ እኔ የማውቀው ነገር ቢኖር እሱ ጠርቶኝ የፈለጋችሁት ነገር የማይቻል ነው ማለቱን ነው፣ "
"የእናቴ አስከሬን መቃጠሉን የሚያውቅ ከሆነ ለምን እራሱ አልነገረኝም?"
"የእኔ ግምት አንቺ ለዜናው የምታሳይውን ትዕይንት ማየት ስለማይፈልግ ይመስለኛል "
"አዎ" ብላ ትኩረቷን ሳትከፋፍል አጉረመረመች፣
"ሁከትን አይወድም። ››
በዝምታ ተመለከተችው። "ቆሻሻ ስራውን እንድትሰራለት ነው አይደል የላከህ ?። ››ነበር ያለችው፡፡
ኩማንደሩ አስተያየት ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆኑ ጓንቱን አንስቶ አጠለቀ…ኮፍያውንም መልሶ አደረገ ።
"አሁን ደንግጠሻል ..ግን አይዞሽ ደህና ትሆኚያለሽ?"
"ደህና ነኝ።"
"ጥሩ ››
ጥቋቁር አይኖቿ በእንባ ተሞሉ እና አፏ በትንሹ ተንቀጠቀጠ። ድንገት ወደእሱ ተንቀሳቀሰችና እጆቿን ከወገብዋ ጋር አጣበቀች..እና ተሸጎጠችበት። ያን አጥር እንደገና ከመገንባቷ በፊት፣ እጆቹን አንሸራትቶ ወደ እሱ ጎተታት። እሷ ሞቃት ትንፋሽ እና ጥሩ መዓዛ ነበራት በሀዘኗ ውስጥ ደካማ ሆናለች. እጆቿ ሳይጨነቁ ወደ ጎን ተንጠልጥለዋል።
"ኦ አምላኬ እባክህ በዚህ ፈተና ውስጥ እንዳልፍ አታድርገኝ" ስትል በሹክሹክታ ተናገረች እና ጡቶቿ ሲንቀጠቀጡ ተሰማት። እንባዋን ሲንጠባጠብ በልብሱ አልፎ እስኪሰማው ድረስ ጭንቅላቷን ወደ እሱ አስጠጋች። ፀጉሯን የጠቀለለችበት ፎጣ ተንሸራቶ መሬት ላይ ወደቀ። ፀጉሯ እርጥብ ነበር። በወቅቱ እሷን መሳም እንደሌለበት ለራሱ እየተናገረ ነው… ነገር ግን ከንፈሩ ፀጉሯን ከዚያም የአንገቷ ስር ሽታን ወደውስጡ እየማገ ስለሆነ እየደነዘዘ ነበር፡።በዚያን ጊዜ፣ ከባድ የፍትወት ስሜት አቅበጠበጠው፣ እናም በጣም
❤42👍6
ኃይለኛ ስለነበር መቋቋም መቻሉ ለእሱ ድንቅ ነበር።ይልቁንስ ከእንደዚያ አይነት መቃተት በኋላ እንደ እባብ ፈልቅቆ ከስሯ መውጣቱ እንደ ቂም እየተሰማው ሄደ። ከእሷ ጋር መቆየት መፈለጉ ምንም ጥያቄ አልነበረውም. ግን ደግሞ እሱ ለራሱ ማመን እስኪያቅተው ድረስ ራሱን መቋጣጠር ቻለ። በጠንካራ ስሜት እሷን መሳም ፈልጎ ነበር።ነጭ ጋወኗን ከላዮ ላይ ገፎ ጥሎ እርቃኗን ሊያስቀራት ፈልጎ ነበር፡፡፡ወገቧን ጨምቆ ይዞ በአየር ላይ ሊያንሳፍፍፋት ፈልጎ ነበር….በትከሻው ተሸክሞ ወደመኝታ ቤቷ ይዞት ሊገባ ፈልጎ ነበር…..ብዙ ብዙ ነገር ማድረግ ፈልጎ ነበር…ግን ምንም ነገር አላደረገም፡፡
ከእሷ ጋር በፍቅር ለመቋራኘት በጣም አርጅቷል ። አስደሳች የወሲብ ቅዠቶች እንደሆነ አሰበ ….ጠንካራ, ብስል ቀይ የጡት ጫፎች ለስላሳ ፣ ጥቁር ፀጉር። ጭኖቿ ለስላሳ ይሆናሉ….እና ….. ለአፍታ ዓይኑን ጨመቀ።
እሷ ከእሱ በአሥራ ስምንት ዓመት የምታንስ ሴት ነች፡፡በዛ ላይ የሰሎሜ ልጅ ነች፣ እና በዕድሜው አባቷ ሊሆን ይችላል፣፡፡ አባቷ የመሆን አጋጣሚም ነበረው ። ያንን ማወቁ ሆዱ ትንሽ እንዲረበሽ አድርጎት ነበር ።ብቻ እንደምንም ያለ የሌለ አቅሙን አጠራቅሞ ተሰናብቷት ወደቤቱ መሄድ ቻለ…ልቡ ግን ይሄው ዛሬ በሁተኛ ቀኑም እዛው እሷ ቤት እንደተቸነከረ ነው፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ከእሷ ጋር በፍቅር ለመቋራኘት በጣም አርጅቷል ። አስደሳች የወሲብ ቅዠቶች እንደሆነ አሰበ ….ጠንካራ, ብስል ቀይ የጡት ጫፎች ለስላሳ ፣ ጥቁር ፀጉር። ጭኖቿ ለስላሳ ይሆናሉ….እና ….. ለአፍታ ዓይኑን ጨመቀ።
እሷ ከእሱ በአሥራ ስምንት ዓመት የምታንስ ሴት ነች፡፡በዛ ላይ የሰሎሜ ልጅ ነች፣ እና በዕድሜው አባቷ ሊሆን ይችላል፣፡፡ አባቷ የመሆን አጋጣሚም ነበረው ። ያንን ማወቁ ሆዱ ትንሽ እንዲረበሽ አድርጎት ነበር ።ብቻ እንደምንም ያለ የሌለ አቅሙን አጠራቅሞ ተሰናብቷት ወደቤቱ መሄድ ቻለ…ልቡ ግን ይሄው ዛሬ በሁተኛ ቀኑም እዛው እሷ ቤት እንደተቸነከረ ነው፡፡
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍41❤11
#ቋጠሮ_ሲፈታ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
አለም መተኛት አቅቷት እየተገለበጠች ባለችበት ጊዜ ነበር ስልኩ የጮኸው፡፡ሰዓቱ እኩለ ለሊት በመጠጋቱ የተነሳ ጥሪው በጣም ነበር ያስደነገጣት ። የራስጌ መብራቱን በማብራት የስልኩን እጄታ አነሳችና ጆረዋ ላይ ለጥፋ ጎላ ባለ ድምፅ "ጤና ይስጥልኝ" አለች፡፡ቀደም ብሎ ስታለቅስ ስለቆየች ድምጿ የሻከረ ነበር
"ሰላም ››መለሰላት፡፡
"አወቅሽኝ ወ.ሪት አለም "
ልቧ በደስታ ዘለለ፣"አንተ እንደገና? በዚህ ውድቅት ለሊት ከእንቅልፍ ያስነሳኸኝ ደህና ነገር ልትነግረኝ እንደሆነ ተስፋ አደርጋለሁ" አለችው።እምቢተኛ ምስክሮች ብዙ ጊዜ የሚናገሩትን ነገር አስፈላጊነት ሲጠቀስላቸው ለመናገር እንደሚበረታቱ ከልምድ ታዝባለች፡፡
"ከኔ ጋር ድብብቆሽ አትጫወቺ …. ማወቅ የምትፈልጊውን በጠቅላላ አውቃለሁ። "
"ለምሳሌ ምን?"
"ለምሳሌ እናትሽን ማን እንደገደላት››
አለም አተነፋፈስዋን በመቆጣጠር ላይ ትኩረት አደረገች።
" ይመስለኛል ዜናው አስደምሞሻል››
"ታዲያ ንገረኝ ማን ነበር?"
"እመቤት ደደብ እመስልሻለሁ እንዴ? ኩማንደሩ ቀደም ሲል ስልክሽን አለማስጠለፉን በምን አውቃለው ?"
"ይመስለኛል….በጣም ብዙ ፊልሞችን አይተሃል?››
‹‹ተረቡን አቁሚና ይልቅ በፅሞና አድምጪኝ ….ነገ ማታ አንድ ሰዓት ሸዋበር የሚገኘው ደንበል ሆቴል እንገናኝ" በማለት ሰዓቱንና ቦታውን ነገራት፡፡
"እንዴት ላውቅህ እችላለሁ?"
"እኔ አውቅሻለሁ"
ሌላ ነገር ከመናገሯ በፊት ስልኩን ዘጋው። አለም በአልጋው ጠርዝ ላይ ለጥቂት ጊዜ ተቀምጣ ጨለማውን እያየች ደርቃ ቀረች። ልትጎዳ እንደምትችል የነገራትን የኩማንደሩ ማስጠንቀቂያ አስታወሰች። የእርሷ ምናባዊ አእምሮ በሴት ላይ ብቻ ሊደርስ የሚችለውን አሰቃቂ ነገር ሁሉ አስተናገደ። በተኛችበት ሆና በላብ ተጠምቀው ነበር።
///
የከተማው የፖሊስ አዛዥ እንፋሎት የሚትገለግበትን ቡናውን አንስቶ ጠጣ። ምላሱን አቃጠለው። ግን ግድ አልነበረውም። በጣም በከፋ መንገድ የካፌይን ማነቃቂያ ያስፈልገዋል
‹‹ስለማን ነው የምናወራው?›› ሲል በግል ቢሮው ደጃፍ ላይ ቆሞ የነበረውን ምክትሉን ጠየቀ ..
" ስለአቃቢ ህግ ፅ/ቤት ነው››
"ስለ ወ.ሪት አለም እያወራህ ነው ?" ምክትሉ መለሰ " አዎ ጌታዬ ስለእሷ ነው።" "እሺ ምን አዲስ ነገር አለ?"
" የእናቷን የሬሳ ምርመራ መዝገብ አስወጥታ ዠለመመርመር ወደ ተክለሀይማኖት ቤ/ክርስቲያን ሄዳለች ››
"ምን?"
"አዎ ጌታዬ እንዲከታተሏት የመደብናቸው ፖሊሶች ናቸው ደውለው የነገሩኝ፡፡››
‹‹በል አሁኑኑ ደውልላቸውና ወደእነሱ እየመጣሁ እንደሆነ ንገራቸው››
ገመዶ ኮቱን ከተሰቀለበት አንስቶ ቢሮውን ለቆ ወጣ…፡፡ ትምህርት ቤቶችን እና አብዛኛዎቹን የንግድ ድርጅቶች እንዲዘጉ ያደረጋቸውን የፀጥታ ችግር ቢኖርም ግድ አል ነበረውም። ሰልፈኛውን እየሰነጠቀ እና ወንበር እያሳበረ ወደሆስፒታል ነዳው፡፡
"የት ነው ያለችው?" እንደደረሰ ኩማንደሩ ጮኸ፣..አንድ አነስተኛ ቢሮ መሰል ክፍል ውስጥ ቁጭ ብላ ከአስተዳዳሪው ጋር ስታወራ ተመለከታ…ወደእዛው ተንደርድሮ ሄደ፡፡
ምንም ፍቃድ ሳይጠይቅ ሰተት ብሎ ገባና " ምን እየሰራሽ ነው ?"አንቧረቀባት፡፡ "እንደምን አደርክ ኩማንደር"አለችው ለስለስ ብላ፡፡
"ጥያቄዬን መልሺልኝ?"
‹‹ምን እያደረኩ እንደሆነማ በደንብ ታውቃለህ?››
"በአንቺ ምክንያት ሴትዮዬ ስራዬን መስራት አልቻልኩም….ከተማዋ በበጥባጭ ጎረምሶች ተረብሻ ያንን ማረጋጋት ሲጠበቅብኝ እኔ አንቺን በየመቃብር ቤቱ እከታተልሻል። ለማንኛውም እንዴት እዚህ ደረስሽ?"
" እየነዳሁ።"
በንዴት በጠረጴዛው ላይ የተበተኑትን ፋይሎች አያመለከተ"ይህ ሁሉ ምንድን ነው?"ሲል ጠየቃት፡፡
" መዛግብት ነዋ…..እናቴ ስትቀበር ለአገልግሎት የተከፈሉ ካርኒዎች እና መሰል መረጃዎች ሊኖሩ ስለሚችሉ ያንን እያዩልኝ ነው፣ ፡፡
"አስገድደሽው ነው?::"
‹‹እኔ እንደዚህ ያለ ነገር አላደረኩም..እንዴት ነው ምታስበኝ…?ደፍሬ አባቶቼን የማስገድድ ይመስልሀል?."
" ታዲያ የፍተሻ ማዘዣ ፍቃደሽን አልጠየቁሽም?"
ካህኑ‹‹ልጆቼ ይቅርታ እስኪ እናንተ አውሩ እኔ መጣሁ››ብለው ከመቀመጫቸው ተነሱና ክፍሉን ለቀውላቸው ወጡ … ገመዶ ወደሷ ቀረበና በንዴት ክንዷን ጨምድዷ ያዘ፡፡
‹‹ምን እያደረክ ነው?››
‹‹ቄሱን የሆነ ነገር ብዬ ከማስቀየሜ በፊት ቀጥ ብለሽ ቦታውን ለቀሽ ውጪ››
‹‹ለምንድነው እንደዛ የምታደርገው?››
‹‹ነገርኩሽ እኮ..አሁን ተከትለሺኝ ትሄጂያለሽ ወይስ…የማደርገውን ቆመሽ ትመለከቻለሽ?››
ትኩር ብላ አየችው … ፊቱ እንደ ተራራ ሰንሰለታማና ወጣ ገባ ነው፣በአጭሩ ቋጥኝ ይመስላል፣ ነገር ግን እስካሁን ካጋጠሟት በጣም ማራኪ ወንዶች ውስጥ አንዱ ነው።አብረው በሚሆኑበት ጊዜ ሁሉ፣ ስለ እሱ፣ ስለ ሰውነቱ ታስባለች፡፡ የእሷ ለእሱ ያላት መስህብ ሥነ ምግባር የጎደለው እና ከዛም አልፎ እንዝላልነት እንደሆነ ታውቃለች። መጀመሪያ የእናቷ ፍቅረኛ ነበረ።ያንን በደንብ ታውቃለች ..ሆኖም ብዙ ጊዜ እሱን ለመንካት ትፈልግ ነበር። ትናንት ማታ በምታለቅስበት ጊዜ እንዲያባብላት ትፈልግ ነበር። ወደመኝታ ቤቷ ተከትሏት እንዲገባም ፈልጋ ነበር…ደግነቱ እሱ በተሻለ ብቃት እራሱን የመቆጣጠር ችሎታ ነበረው እና ምንም ሳያደርግ ትቷት ሄደ።
‹‹የሰሎሜ ሬሳ እንደተቃጠለ ነግሬሻለሁ።››
"አንተ እና ዳኛው ጭንቅላታችሁን አንድ ላይ አድርጋችሁ እያሻጠራችሁ መሆኑን ማወቄ የተመቸኝ ይመስልሀል?።››
"ነገሮችን መገመት ያስደስትሻል?."
"ጁኒየር እናቴ ሬሳ መቃጠሏን ለምን አልነገረኝም?እንደተቀበረች ነበር የነገረኝ ››
‹‹እኔ እየዋሸሁሽ ይምስልሻል….?ለምን ብዬ?" " አስከሬኑ እንዳይወጣ ስለምትፈልግ ነዋ።"
"ሬሳው እንዳይወጣ ለምንድነው የምፈልገው? በእኔ ላይ ምን ለውጥ ያመጣል?"
ፍርጥም ብላ "የእድሜ ልክ እስራት" በማለት መለሰችለት፡፡ "የፎረንሲክ ሪፖርቱ አንተን ነፍሰ ገዳይ መሆንህን የሚያመለክት ፍንጭ ከሰጠን ወደወህኒ መወርወርህ የማይቀር ነው።››
" “አህ...” አለ..ደም ስሯቹ ሲግተረተር እየታዘበች ነው፡፡ "አንቺ ጠበቃ አይደለሽም, ጠንቋይ አዳኝ ነሽ."
"ወንጀል ባይኖር ኖሮ ያ እውነት ሊሆን ይችላል….ግን አንድ ሰው ወደዚያ በረት ውስጥ ገብቶ እናቴን ወግቶ ገድሏታል..እና እስከአሁን ለጥፋቱ የሚመጥን ቅጣት አላገኘም።››
"በእስክሪፕት ደረጃ ትክክል ነሽ" አለ እየተሳለቀ።
"ጋሽ ፍሰሀ ፣ ጁኒየር ወይስ እኔ የቀዶ ጥገና መሳሪያ ይዘን እናትሽን እንደወጋናት ነው ግምትሽ? ለምን በባዶ እጃችን አንገቷን አንቀን አንገድላትም??"
"ሁላችሁም ጎበዝ ስለሆናችሁ።ከመካከላችሁ ወንጀሉን የፈፀመው ሰው እንደዛ ያደረገው ወንጀሉን የአእምሮ ሚዛናዊ የተዛባ ሰው ያደረገው እንዲመስል ፈልጎ ነው።››
‹‹አመንሽም አላመንሽም …እኔ አላደረግኩም
"በብስጭት መለሰላት፡፡
"ታዲያ ማን እንዳደረገው ማወቅ አትፈልግም? ወይስ ነፍሰ ገዳዩ የምትወደው ሌላ ሰው እንዳይሆን ትፈራለህ ?"ስትል ሞጋች ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹አይ ማወቅ አልፈልግም" ሲል በአጽንኦት መለሰላት፡፡
"እኔ ግን ገዳዩን እስካገኝ ድረስ ምርመራዬን አላቋርጥም..››
ሊመልስላት አፉን ሲከፍት አንድ ግራ እግራቸው ሸንከል የሚል አዛውንት አንድ ያረጀች መዝገብ ይዘው ወደውስጥ ሲገቡ ሲመለከት አፉን መልሶ ከደነ፡፡
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
አለም መተኛት አቅቷት እየተገለበጠች ባለችበት ጊዜ ነበር ስልኩ የጮኸው፡፡ሰዓቱ እኩለ ለሊት በመጠጋቱ የተነሳ ጥሪው በጣም ነበር ያስደነገጣት ። የራስጌ መብራቱን በማብራት የስልኩን እጄታ አነሳችና ጆረዋ ላይ ለጥፋ ጎላ ባለ ድምፅ "ጤና ይስጥልኝ" አለች፡፡ቀደም ብሎ ስታለቅስ ስለቆየች ድምጿ የሻከረ ነበር
"ሰላም ››መለሰላት፡፡
"አወቅሽኝ ወ.ሪት አለም "
ልቧ በደስታ ዘለለ፣"አንተ እንደገና? በዚህ ውድቅት ለሊት ከእንቅልፍ ያስነሳኸኝ ደህና ነገር ልትነግረኝ እንደሆነ ተስፋ አደርጋለሁ" አለችው።እምቢተኛ ምስክሮች ብዙ ጊዜ የሚናገሩትን ነገር አስፈላጊነት ሲጠቀስላቸው ለመናገር እንደሚበረታቱ ከልምድ ታዝባለች፡፡
"ከኔ ጋር ድብብቆሽ አትጫወቺ …. ማወቅ የምትፈልጊውን በጠቅላላ አውቃለሁ። "
"ለምሳሌ ምን?"
"ለምሳሌ እናትሽን ማን እንደገደላት››
አለም አተነፋፈስዋን በመቆጣጠር ላይ ትኩረት አደረገች።
" ይመስለኛል ዜናው አስደምሞሻል››
"ታዲያ ንገረኝ ማን ነበር?"
"እመቤት ደደብ እመስልሻለሁ እንዴ? ኩማንደሩ ቀደም ሲል ስልክሽን አለማስጠለፉን በምን አውቃለው ?"
"ይመስለኛል….በጣም ብዙ ፊልሞችን አይተሃል?››
‹‹ተረቡን አቁሚና ይልቅ በፅሞና አድምጪኝ ….ነገ ማታ አንድ ሰዓት ሸዋበር የሚገኘው ደንበል ሆቴል እንገናኝ" በማለት ሰዓቱንና ቦታውን ነገራት፡፡
"እንዴት ላውቅህ እችላለሁ?"
"እኔ አውቅሻለሁ"
ሌላ ነገር ከመናገሯ በፊት ስልኩን ዘጋው። አለም በአልጋው ጠርዝ ላይ ለጥቂት ጊዜ ተቀምጣ ጨለማውን እያየች ደርቃ ቀረች። ልትጎዳ እንደምትችል የነገራትን የኩማንደሩ ማስጠንቀቂያ አስታወሰች። የእርሷ ምናባዊ አእምሮ በሴት ላይ ብቻ ሊደርስ የሚችለውን አሰቃቂ ነገር ሁሉ አስተናገደ። በተኛችበት ሆና በላብ ተጠምቀው ነበር።
///
የከተማው የፖሊስ አዛዥ እንፋሎት የሚትገለግበትን ቡናውን አንስቶ ጠጣ። ምላሱን አቃጠለው። ግን ግድ አልነበረውም። በጣም በከፋ መንገድ የካፌይን ማነቃቂያ ያስፈልገዋል
‹‹ስለማን ነው የምናወራው?›› ሲል በግል ቢሮው ደጃፍ ላይ ቆሞ የነበረውን ምክትሉን ጠየቀ ..
" ስለአቃቢ ህግ ፅ/ቤት ነው››
"ስለ ወ.ሪት አለም እያወራህ ነው ?" ምክትሉ መለሰ " አዎ ጌታዬ ስለእሷ ነው።" "እሺ ምን አዲስ ነገር አለ?"
" የእናቷን የሬሳ ምርመራ መዝገብ አስወጥታ ዠለመመርመር ወደ ተክለሀይማኖት ቤ/ክርስቲያን ሄዳለች ››
"ምን?"
"አዎ ጌታዬ እንዲከታተሏት የመደብናቸው ፖሊሶች ናቸው ደውለው የነገሩኝ፡፡››
‹‹በል አሁኑኑ ደውልላቸውና ወደእነሱ እየመጣሁ እንደሆነ ንገራቸው››
ገመዶ ኮቱን ከተሰቀለበት አንስቶ ቢሮውን ለቆ ወጣ…፡፡ ትምህርት ቤቶችን እና አብዛኛዎቹን የንግድ ድርጅቶች እንዲዘጉ ያደረጋቸውን የፀጥታ ችግር ቢኖርም ግድ አል ነበረውም። ሰልፈኛውን እየሰነጠቀ እና ወንበር እያሳበረ ወደሆስፒታል ነዳው፡፡
"የት ነው ያለችው?" እንደደረሰ ኩማንደሩ ጮኸ፣..አንድ አነስተኛ ቢሮ መሰል ክፍል ውስጥ ቁጭ ብላ ከአስተዳዳሪው ጋር ስታወራ ተመለከታ…ወደእዛው ተንደርድሮ ሄደ፡፡
ምንም ፍቃድ ሳይጠይቅ ሰተት ብሎ ገባና " ምን እየሰራሽ ነው ?"አንቧረቀባት፡፡ "እንደምን አደርክ ኩማንደር"አለችው ለስለስ ብላ፡፡
"ጥያቄዬን መልሺልኝ?"
‹‹ምን እያደረኩ እንደሆነማ በደንብ ታውቃለህ?››
"በአንቺ ምክንያት ሴትዮዬ ስራዬን መስራት አልቻልኩም….ከተማዋ በበጥባጭ ጎረምሶች ተረብሻ ያንን ማረጋጋት ሲጠበቅብኝ እኔ አንቺን በየመቃብር ቤቱ እከታተልሻል። ለማንኛውም እንዴት እዚህ ደረስሽ?"
" እየነዳሁ።"
በንዴት በጠረጴዛው ላይ የተበተኑትን ፋይሎች አያመለከተ"ይህ ሁሉ ምንድን ነው?"ሲል ጠየቃት፡፡
" መዛግብት ነዋ…..እናቴ ስትቀበር ለአገልግሎት የተከፈሉ ካርኒዎች እና መሰል መረጃዎች ሊኖሩ ስለሚችሉ ያንን እያዩልኝ ነው፣ ፡፡
"አስገድደሽው ነው?::"
‹‹እኔ እንደዚህ ያለ ነገር አላደረኩም..እንዴት ነው ምታስበኝ…?ደፍሬ አባቶቼን የማስገድድ ይመስልሀል?."
" ታዲያ የፍተሻ ማዘዣ ፍቃደሽን አልጠየቁሽም?"
ካህኑ‹‹ልጆቼ ይቅርታ እስኪ እናንተ አውሩ እኔ መጣሁ››ብለው ከመቀመጫቸው ተነሱና ክፍሉን ለቀውላቸው ወጡ … ገመዶ ወደሷ ቀረበና በንዴት ክንዷን ጨምድዷ ያዘ፡፡
‹‹ምን እያደረክ ነው?››
‹‹ቄሱን የሆነ ነገር ብዬ ከማስቀየሜ በፊት ቀጥ ብለሽ ቦታውን ለቀሽ ውጪ››
‹‹ለምንድነው እንደዛ የምታደርገው?››
‹‹ነገርኩሽ እኮ..አሁን ተከትለሺኝ ትሄጂያለሽ ወይስ…የማደርገውን ቆመሽ ትመለከቻለሽ?››
ትኩር ብላ አየችው … ፊቱ እንደ ተራራ ሰንሰለታማና ወጣ ገባ ነው፣በአጭሩ ቋጥኝ ይመስላል፣ ነገር ግን እስካሁን ካጋጠሟት በጣም ማራኪ ወንዶች ውስጥ አንዱ ነው።አብረው በሚሆኑበት ጊዜ ሁሉ፣ ስለ እሱ፣ ስለ ሰውነቱ ታስባለች፡፡ የእሷ ለእሱ ያላት መስህብ ሥነ ምግባር የጎደለው እና ከዛም አልፎ እንዝላልነት እንደሆነ ታውቃለች። መጀመሪያ የእናቷ ፍቅረኛ ነበረ።ያንን በደንብ ታውቃለች ..ሆኖም ብዙ ጊዜ እሱን ለመንካት ትፈልግ ነበር። ትናንት ማታ በምታለቅስበት ጊዜ እንዲያባብላት ትፈልግ ነበር። ወደመኝታ ቤቷ ተከትሏት እንዲገባም ፈልጋ ነበር…ደግነቱ እሱ በተሻለ ብቃት እራሱን የመቆጣጠር ችሎታ ነበረው እና ምንም ሳያደርግ ትቷት ሄደ።
‹‹የሰሎሜ ሬሳ እንደተቃጠለ ነግሬሻለሁ።››
"አንተ እና ዳኛው ጭንቅላታችሁን አንድ ላይ አድርጋችሁ እያሻጠራችሁ መሆኑን ማወቄ የተመቸኝ ይመስልሀል?።››
"ነገሮችን መገመት ያስደስትሻል?."
"ጁኒየር እናቴ ሬሳ መቃጠሏን ለምን አልነገረኝም?እንደተቀበረች ነበር የነገረኝ ››
‹‹እኔ እየዋሸሁሽ ይምስልሻል….?ለምን ብዬ?" " አስከሬኑ እንዳይወጣ ስለምትፈልግ ነዋ።"
"ሬሳው እንዳይወጣ ለምንድነው የምፈልገው? በእኔ ላይ ምን ለውጥ ያመጣል?"
ፍርጥም ብላ "የእድሜ ልክ እስራት" በማለት መለሰችለት፡፡ "የፎረንሲክ ሪፖርቱ አንተን ነፍሰ ገዳይ መሆንህን የሚያመለክት ፍንጭ ከሰጠን ወደወህኒ መወርወርህ የማይቀር ነው።››
" “አህ...” አለ..ደም ስሯቹ ሲግተረተር እየታዘበች ነው፡፡ "አንቺ ጠበቃ አይደለሽም, ጠንቋይ አዳኝ ነሽ."
"ወንጀል ባይኖር ኖሮ ያ እውነት ሊሆን ይችላል….ግን አንድ ሰው ወደዚያ በረት ውስጥ ገብቶ እናቴን ወግቶ ገድሏታል..እና እስከአሁን ለጥፋቱ የሚመጥን ቅጣት አላገኘም።››
"በእስክሪፕት ደረጃ ትክክል ነሽ" አለ እየተሳለቀ።
"ጋሽ ፍሰሀ ፣ ጁኒየር ወይስ እኔ የቀዶ ጥገና መሳሪያ ይዘን እናትሽን እንደወጋናት ነው ግምትሽ? ለምን በባዶ እጃችን አንገቷን አንቀን አንገድላትም??"
"ሁላችሁም ጎበዝ ስለሆናችሁ።ከመካከላችሁ ወንጀሉን የፈፀመው ሰው እንደዛ ያደረገው ወንጀሉን የአእምሮ ሚዛናዊ የተዛባ ሰው ያደረገው እንዲመስል ፈልጎ ነው።››
‹‹አመንሽም አላመንሽም …እኔ አላደረግኩም
"በብስጭት መለሰላት፡፡
"ታዲያ ማን እንዳደረገው ማወቅ አትፈልግም? ወይስ ነፍሰ ገዳዩ የምትወደው ሌላ ሰው እንዳይሆን ትፈራለህ ?"ስትል ሞጋች ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹አይ ማወቅ አልፈልግም" ሲል በአጽንኦት መለሰላት፡፡
"እኔ ግን ገዳዩን እስካገኝ ድረስ ምርመራዬን አላቋርጥም..››
ሊመልስላት አፉን ሲከፍት አንድ ግራ እግራቸው ሸንከል የሚል አዛውንት አንድ ያረጀች መዝገብ ይዘው ወደውስጥ ሲገቡ ሲመለከት አፉን መልሶ ከደነ፡፡
❤43👍1
"ይመስለኛል ይህን ነው የምትፈልገው? የድሮ ፋይሎች ካሉበት በመከራ ነው ፈልጌ ያገኘሁት….በዛን ወቅት ካርኒ አንጠቀምም ነበር…ግን የሞች ስምን …የተቀበረበትን ቀን እና የከፈለውን ብር የመሳሰሉትን መረጃዎች በዚህ መዝገብ እንመዘግብ ነበር›› በማለት
የሚሰነፍጥ አይነት ሽታ ያለውን መዝገብ አቀበሏት….ኩማንደሩ መዝገቡን ተቀብሎ ቀዳዶ ለመጣል ነበር ፍላጎቱ… ግን እንደምንም ራሱን ተቆጣጠረ እና በዝምታ የሚሆነው ያይ ጀመር..በመስገብገብ ተቀበለችን እየገለጠች እያንዳንዱ ገፅ ላይ ማየት ጀመረች ፡፡
አገኘሁት..ይሄውና…..ስሟ የተቀበረችበት ቀን……ምርምር በሚለው ቦታ ላይ ..ሬሳው ተቃጥሎ ስለነበረ ቀብሩ የመታሰቢያ ነው››ይላል፡፡በድንጋጤ ጭንቅላቷን ያዘች፡፡
በብስጭት ሰውነቷ እየተቃጠለ ነበር፣…
"አያቴ ለምን ይህን አልተናገረችም?"ይህንን ጥያቄ ለሁለተኛ ጊዜ ስትጠይቀው ነው፡፡ "ምናልባት ጠቃሚ ነው ብላ አላሰበችም ይሆናል."
በድንገት ወደ ፊት ቀረበች፣ ክርኖቿን ጠረጴዛው ላይ አሳርፋ አገጮን በሁለት እጆቿ ደገፈች። ሆዷ በጣም ተንቦጫቦጨ። ትኩስ እንባ ከአይኖቾ ረገፉ
"እግዚአብሔር ሆይ፣ ይህ በሽታ ነው፣ ግን ማወቅ አለብኝ።አዎ እውነቱን ማወቅ አለብኝ።"ትንሽ ትንፋሽ ከወሰደች በኋላ መዝገቡን እንደገና ከፈተች እና የተለያዩ ቅጾችን ማገላበጥ ጀመረች። አንዱን እያነበበች ትንፋሿን በደንብ ወሰደች።
"ምንድነው ይሄ?፧"
"ምኑ ?"
"በመጨረሻ ላይ ያለው ያስቀባሪ ፊርማውን ተመልከት." "ጋሽ ፍሰሀ ነው"
"ይህ ማለት በወቅቱ ሁሉንም ወጪዎች ሆነ የቀብር ስርአቱን ይቆጣጠርና ክፍያውን ሁሉ ይከፍል የነበረው እሱ ነው ማለት ነው…እና ይሄ አይገርምህም?››
"ለምን ይገርመኛል።
‹‹እናቴ የእሱ ንብረት በሆነ መሬት ላይ ነው የሞተችው…ከዛ ጀምሮ ሆስፒታል ገብታ
..ከዛም እስክትቀበር ድረስ እያንዳንዱ በሆነው ነገር ሁሉ በእሱ እይታ ውስጥ ነበር….ወይ የሆነውን ነገር ሁሉ ያደረገው እራሱ ነው ወይንም ደግሞ ማን ምን እንዳደረገ በትክክል ያውቃል፡››
‹‹ምን አይነት ቆሻሻ ጭንቅላት ነው ያለሽ…?በአንቺ ቦታ ሌላ ሰው ቢሆን ኖሮ እናቴን ስላስቀበረልኝና አስፈላጊውን ነገር ሁሉ ስላደረገ እግዚያብሄር ይስጠው ብለው ነበር የሚያመሰግኑት››
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
የሚሰነፍጥ አይነት ሽታ ያለውን መዝገብ አቀበሏት….ኩማንደሩ መዝገቡን ተቀብሎ ቀዳዶ ለመጣል ነበር ፍላጎቱ… ግን እንደምንም ራሱን ተቆጣጠረ እና በዝምታ የሚሆነው ያይ ጀመር..በመስገብገብ ተቀበለችን እየገለጠች እያንዳንዱ ገፅ ላይ ማየት ጀመረች ፡፡
አገኘሁት..ይሄውና…..ስሟ የተቀበረችበት ቀን……ምርምር በሚለው ቦታ ላይ ..ሬሳው ተቃጥሎ ስለነበረ ቀብሩ የመታሰቢያ ነው››ይላል፡፡በድንጋጤ ጭንቅላቷን ያዘች፡፡
በብስጭት ሰውነቷ እየተቃጠለ ነበር፣…
"አያቴ ለምን ይህን አልተናገረችም?"ይህንን ጥያቄ ለሁለተኛ ጊዜ ስትጠይቀው ነው፡፡ "ምናልባት ጠቃሚ ነው ብላ አላሰበችም ይሆናል."
በድንገት ወደ ፊት ቀረበች፣ ክርኖቿን ጠረጴዛው ላይ አሳርፋ አገጮን በሁለት እጆቿ ደገፈች። ሆዷ በጣም ተንቦጫቦጨ። ትኩስ እንባ ከአይኖቾ ረገፉ
"እግዚአብሔር ሆይ፣ ይህ በሽታ ነው፣ ግን ማወቅ አለብኝ።አዎ እውነቱን ማወቅ አለብኝ።"ትንሽ ትንፋሽ ከወሰደች በኋላ መዝገቡን እንደገና ከፈተች እና የተለያዩ ቅጾችን ማገላበጥ ጀመረች። አንዱን እያነበበች ትንፋሿን በደንብ ወሰደች።
"ምንድነው ይሄ?፧"
"ምኑ ?"
"በመጨረሻ ላይ ያለው ያስቀባሪ ፊርማውን ተመልከት." "ጋሽ ፍሰሀ ነው"
"ይህ ማለት በወቅቱ ሁሉንም ወጪዎች ሆነ የቀብር ስርአቱን ይቆጣጠርና ክፍያውን ሁሉ ይከፍል የነበረው እሱ ነው ማለት ነው…እና ይሄ አይገርምህም?››
"ለምን ይገርመኛል።
‹‹እናቴ የእሱ ንብረት በሆነ መሬት ላይ ነው የሞተችው…ከዛ ጀምሮ ሆስፒታል ገብታ
..ከዛም እስክትቀበር ድረስ እያንዳንዱ በሆነው ነገር ሁሉ በእሱ እይታ ውስጥ ነበር….ወይ የሆነውን ነገር ሁሉ ያደረገው እራሱ ነው ወይንም ደግሞ ማን ምን እንዳደረገ በትክክል ያውቃል፡››
‹‹ምን አይነት ቆሻሻ ጭንቅላት ነው ያለሽ…?በአንቺ ቦታ ሌላ ሰው ቢሆን ኖሮ እናቴን ስላስቀበረልኝና አስፈላጊውን ነገር ሁሉ ስላደረገ እግዚያብሄር ይስጠው ብለው ነበር የሚያመሰግኑት››
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍27❤16