#ባለቀሱት_ቀናሁ
ቀናሁኝ ቀናሁኝ ቀናሁኝ በነሱ
እንባቸው እንደጕርፍ
ወርዶ ባለቀሱ
ቀናሁኝ ቀናሁኝ ቀናሁኝ በነሱ
ከውስጣቸው ወጥቶ
እፎይታን ባገኙ
እኔ ግን . . . እኔ ግን
ሚስጥሬን ታቅፌ
ለሰው ሳልተነፍስ
እህህ ... ታዬን ይዤ
ለሊቱ ረዝሞብኝ
በዝቶብኝ ችግሬ
ማልቀስ መጮህ ሳልችል
አለሁ በትካዜ፡፡
ቀናሁኝ ቀናሁኝ ቀናሁኝ በነሱ
እንባቸው እንደጕርፍ
ወርዶ ባለቀሱ
ቀናሁኝ ቀናሁኝ ቀናሁኝ በነሱ
ከውስጣቸው ወጥቶ
እፎይታን ባገኙ
እኔ ግን . . . እኔ ግን
ሚስጥሬን ታቅፌ
ለሰው ሳልተነፍስ
እህህ ... ታዬን ይዤ
ለሊቱ ረዝሞብኝ
በዝቶብኝ ችግሬ
ማልቀስ መጮህ ሳልችል
አለሁ በትካዜ፡፡
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_ሦስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ከዳማሲን_የተላከ_ደብዳቤ
፡
፡
ከትምህርት ቤቱ በስተጀርባ ብቻዬን ሆኜ የዳማሲንን ደብዳቤ ከፈትኩት፡፡ ለማንበብ የሚያስቸግረውን የእጅ ጽሑፉን እንዳየሁ በትምህርት ቤት እንዳለን የጻፈልኝን ደብዳ ቤዎች ሁሉ አስታውሼ ልቤ ታመመ፡፡ ፈጽሞ ግልጽ ስሜት የማይንጸባረቅባቸው፣ ግን ሁሌ በፍቅርና በደግነት፣ በማበረታቻና አድናቆት፣ በግሩም ምክርና ረጋ ያለ ተግሳጽ፣ ስለ ወዳጆቻችን በሚያወሱ ወሬዎችና በብዙ ቀልዶች የተሞሉ ደብዳቤዎቹ ትውስ አሉኝ፡፡ ጀርባዬን በትምህርት ቤቱ ክፍል ግድግዳ ላይ አስደግፌ ተቀምጬ አነብ ጀመር፡፡
ግንቦት 6፣ 1994
ውድ (አባባ፣ እማማ፣ ቪያኒ እና) ኢማኪዩሌ ሁላችንም ከተለያየን አንድ ወር ገደማ ሆነን፡፡ ይሄው የቅዠት ኑሮ እየኖርን ነው፡፡ ሁናቴዎች ከሚያሳዩት ነገር ባሻገር አንድ ዘውግ ሌላውን ፈጽሞ የሚያጠፋው የእግዚአብሔር ፍቃድ ሲሆን ብቻ ይሆናል ብዬ አምናለሁ፡፡ ምናልባት የእኛ ሕይወት ለሩዋንዳ ድኅነት እንዲከፈል ግድ ብሎ ሊሆን ይችላል፡፡ ስለ አንድ ነገር እርግጠኛ ነኝ - እንደገና እንደምንገናኝ በአእምሮዬ ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ የለም፡፡
ከሀገሪቱ ለመውጣት ልሞክር ነው፣ ግን ይሳካልኝ አይሳካልኝ አላውቅም፡፡ በመንገድ ላይ ከገደሉኝ ስለ እኔ አትጨነቁ፤ በሚገባ ጸልያለሁ . . . ለሞትም ተዘጋጅቻለሁ፡፡ ከሩዋንዳ መውጣት ከቻልኩ ሰላም እንደተመለሰ ወዲያውኑ ሁላችሁንም አገኛችኋለሁ፡፡ የደረሰብኝን ሁሉ ቦን
ይነግራችኋል፡፡
የዳማሲን ጓደኛ ቦን በሌላ ጊዜ እንደነገረኝ ወንድሜ ደብዳቤውን እየጻፈ ሳለ እዚህ ሐሳብ ላይ ሲደርስ ዳማሲን ብዕሩን ቁጭ አድርጎ ቀና ብሎ እያየው ‹‹ቦን፣ ወዳጄ እንደሆንክ አውቃለሁ፤ ስሜቴም ሳይጎዳ እንዲቆይ ሞክረሃል፣ አሁን ልትነግረኝ የሚገባህ ሰዓት ላይ ነን - ከቤተሰቤ አባላት የተገደለ አለ እንዴ?›› ቦን ሁቱ ስለሆነ በዘር ጭፍጨፋው ወቅት በነጻነት ይጓጓዝና በአካባቢው ከቱትሲዎች ማንኛቸው እንደተገደሉ ያውቃል፡፡ የወላጆቼንና የቪያኒን ሞት ለራሱ በምስጢር የያዘው ለወንድሜ በጣም ስለሚጠነቀቅለትና ስሜቱን ሳይጎዳ ለመጠበቅ ስለፈለገ ነው፡፡
ዳማሲን በቀጥታ ሲጠይቀው ጊዜ ቦን ከባዱን መርዶ አረዳው፡፡ ጓደኛው የሚወዳቸው የቤተሰቡ አባላት ገና በሕይወት ያሉ እየመሰለው ደብዳቤውን መጻፉን እስኪጨርስ መጠበቅን አልፈለገም፡፡ ስለዚህ ቦን ለዳማሲን አባታችን፣ እናታችንና ታናሽ ወንድማችን እንደተገደሉና እኔ ምናልባት በሕይወት ተርፌ ሊሆን እንደሚችል ይነግረዋል፡፡ ዳማሲን ቀኑን ሙሉ ማለት ይቻላል አልቅሶ እንደነበር የደብዳቤው ቋሚ ምልክት የሆኑት የእንባ ጠብታዎች ይህንን ይመሰክራሉ፡፡
ዳማሲን ኪቩ ሐይቅን ለማቋረጥ ጀልባ ፍለጋ ከመሄዱ በፊት ደብዳቤውን እንደገና አውጥቶ አባባ፣ እማማና ቪያኒ በሚሉት ቃላት ግራና ቀኝ ቅንፎችን አስቀምጦ የሚከተሉትን አረፍተ ነገሮች አከለ፡፡ ኢማኪዩሌ እንድትጠነክሪ እለምንሻለሁ፡፡ እማማ፣ አባባና ቪያኒ መገደላቸውን አሁን ሰማሁ፡፡ በተቻለኝ ፍጥነት ላገኝሽ እሞክራለሁ፡፡ ራስሽን ሳሚልኝ፤ እቀፊልኝም! በጣም የሚወድሽ ወንድምሽ!
ይህ ካነበብኳቸው ነገሮች ሁሉ የሚሠቀጥጠው ነው፡፡ እንባ ባረጠባቸው ቃላት ላይ የጣቶቼን ጫፎች አላወስኳቸውና ይህንን ደብዳቤ ሳላለቅስ ማንበብ እንደማልችል ተረዳሁ፡፡
በኋላ ላይ እንደደረስኩበት ለዘላለም የኔ ጀግና ሆኖ የሚኖረው ቦን ወንድሜን በቤቱ ከቤተሰቡ ፍላጎት በተጻራሪ ሊሸሽገው ሞክሯል፡፡ በዘር ፍጅቱ የመጀመሪያ ቀናት ዳማሲንን በምስጢር ከአልጋው ስር በደኅና በመደበቅ ሊያቆየው ችሎ ነበር፡፡ የቦን ቤተሰብ ግን ያደረገውን ነገር ሲደርስበት ዳማሲንን ለገዳዮቹ እንዲሰጥ ግፊት ያሳድርበታል፡፡
ይባስ ብሎ ቱትሲ ልጆችን በዘውግ ስም ጥሪ ወቅት ማሸማቀቅ የሚወደው ቡሆሮ ከቦን አጎቶች አንዱ ነው፡፡ ቡሆሮ በሀገሪቱ ወስጥ ካሉ ጽንፈኛ ሁቱዎች ውስጥ አንዱ፣ መጥፎና አደገኛ ገዳይ ሆኖ ነበርና ሲጠራጠርበት ጊዜ ቦን ዳማሲንን በጭራሽ ቤት ውስጥ ማቆየት እንደሌለበት ይረዳል፡፡ አንድ ሌሊትም በጣም አምሽቶ በቤተሰቡ መሬት ራቅ ያለ ጥግ ላይ ጉድጓድ ቆፍሮ በዕንጨትና ቅጠላቅጠል ይሸፍነዋል፡፡ ገዳዮቹ በቡሆሮ ተጠቁመው ከመምጣታቸው በፊት ዳማሲንንም በጥንቃቄ ከመኝታ ክፍሉ ያስወጣና በጉድጓዱ ውስጥ ይደብቀዋል ፡፡
ዳማሲን በጉድጓድ ውስጥ ከሦስት ሳምንታት ለበለጠ ጊዜ ያህል ተደብቆ ሳለ ገዳዮቹ በቡሆሮ ውትወታ በተደጋጋሚ የቦንን ቤት አሠሡ፡፡ እነዚህ አራጆች ግን የማይሰለቹ በመሆናቸው የቦንን እያንዳንዷን እንቅስቃሴ ተከታትለው መጨረሻ ላይ ምግብ ወደ ውጪ ይዞ ሲሄድ ያዩታል፡፡ ሸሻጊው ጓደኛውና ተሸሻጊው ዳማሲን ገዳዮቹ ግቢውን ሊያስሱብን ይችላሉ ብለው ሠግተው ዳማሲን የኪቩ ሐይቅን ተሻግሮ ወደ ዛየር እንዲያቀና ይወስናሉ፡፡ (ቦን የቱትሲዎችን ሕይወት ለማትረፍ ሐይቁን የሚያሻግራቸውን አንድ ደግ ሳምራዊ ዐሳ አጥማጅ ሁቱ ያውቃል፡፡) ዳማሲንን ከጉድጓዱ አውጥቶ በየጥላው እየቆዩና ከጥሻ ጥሻ እየተሸጋገሩ ከእኩለ ሌሊት በኋላ ወደ ሐይቁ ሄዱ፡፡ መንገዱ ብዙ ጊዜ በመፍጀቱ ግን የዚያ ሌሊት ጀልባ ታመልጣቸዋለች፡፡
ነጋባቸው፡፡ በመሆኑም ዳማሲን ወደ ቦን ቤት ረጅም መንገድ ተጉዞ ተመልሶ አደጋ ላይ መውደቅን ስላልፈለገ ንሴንጄ በሚባል በሐይቁ አካባቢ የሚኖር የእርሱና የቦን ወዳጅ ቤት ቆየ፡፡ ንሴንጄ ቤተሰባችንን የሚወድ ለዘብተኛ ሁቱ ነው፡፡ አባቴ የብዙ ወንድሞቹን የትምህርት ክፍያ በመክፈል አግዟቸዋል፡፡ ስለሆነም ዳማሲንን ለዚያን ቀን መሸሸግ በመቻሉ ደስ ተሰኘ፡፡
የንሴንጄ ወንድም ሳይመን ግን የወንድሙን ያክል ቸር አልነበረም፡፡ ዳማሲንን በቤታቸው ሲደርስ በፈገግታና በወዳጅነት ተቀብሎታል … በማግስቱ ከሰዓት በኋላ ግን ወንድሜ በተኛበትና ንሴንጄም የጀልባ ጉዞውን ለማመቻቸት በወጣበት ሳይመን ከቤት ሾልኮ ወጥቶ የገዳዮቹን ቡድን ፈልጎ ዳማሲንን አሳልፎ ሰጠው፡፡
ከእራት በፊት ሳይመን ወንድሜን ቀስቅሶ ወደ ዛየር ከመሄድህ በፊት ልብሶችህን ልጠብልህ ይለዋል፡፡ ዳማሲንም ልብሶቹን ሁሉ አወላልቆ በውስጥ ልብስ ብቻ ይቀራል፡፡ ሳይመንም ልብሶቹን ይወስድበታል፡፡ (በኋላ ላይ እንደተናገረው ይህን ያደረገው ወንድሜን ከመሞቱ በፊት ለማሳፈርና ለማሸማቀቅ ፈልጎ ነው፡፡) ልብሶቹን ከወሰደበት በኋላም ሳይመን ወንድሜን በደርዘኖች የሚቆጠሩ ገዳዮች ይጠብቁት ወደነበረበት ወደ ዋናው ቤት ይጠራዋል፡፡ ወንድሜም ላይ ያለ ምኅረት ተረባረቡበት፤ እየደበደቡ ወደ መንገድ ጎተቱት፡፡ ከውስጥ ልብሱም ሌላ ምንም አልለበሰም፡፡ እኛ ቤት ትሠራ የነበረች አንድ ሴት ነገሩን ሁሉ አይታ የዳማሲንን የመጨረሻ ሰዓት ዝርዝር ሁኔታ ነግራኛለች፡፡ ‹‹ቆንጆዋ እህትህ የት ነች?›› ብለው ገዳዮቹ ወንድሜን ይጠይቁታል፡፡ ‹‹የት ነች ኢማኪዩሌ?›› በቤተሰብህ ያሉትን በረሮዎች አስከሬኖች አይተናቸዋል፤ እሷ ግን ገና አልተደረሰባትም… የት ነች? ንገረንና በነጻ እንለቅሃለን፤ ካልነገርከን ግን ሌሊቱን ሙሉ ስንከትፍህ እናድራለን፡፡ በል ኢማኪዩሌ የት እንዳለች ንገረንና በነጻ ትሰናበታለህ፡፡››
ፊቱ የተሰባበረውና ያባበጠው ዳማሲን የከበቡትን ገዳዮች አየት አድርጓቸው በሕይወቴ ሙሉ እንዳደረገልኝ ሁሉ በመጨረሻዋም ቅጽበት ለኔ ቆመልኝ
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_ሦስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ከዳማሲን_የተላከ_ደብዳቤ
፡
፡
ከትምህርት ቤቱ በስተጀርባ ብቻዬን ሆኜ የዳማሲንን ደብዳቤ ከፈትኩት፡፡ ለማንበብ የሚያስቸግረውን የእጅ ጽሑፉን እንዳየሁ በትምህርት ቤት እንዳለን የጻፈልኝን ደብዳ ቤዎች ሁሉ አስታውሼ ልቤ ታመመ፡፡ ፈጽሞ ግልጽ ስሜት የማይንጸባረቅባቸው፣ ግን ሁሌ በፍቅርና በደግነት፣ በማበረታቻና አድናቆት፣ በግሩም ምክርና ረጋ ያለ ተግሳጽ፣ ስለ ወዳጆቻችን በሚያወሱ ወሬዎችና በብዙ ቀልዶች የተሞሉ ደብዳቤዎቹ ትውስ አሉኝ፡፡ ጀርባዬን በትምህርት ቤቱ ክፍል ግድግዳ ላይ አስደግፌ ተቀምጬ አነብ ጀመር፡፡
ግንቦት 6፣ 1994
ውድ (አባባ፣ እማማ፣ ቪያኒ እና) ኢማኪዩሌ ሁላችንም ከተለያየን አንድ ወር ገደማ ሆነን፡፡ ይሄው የቅዠት ኑሮ እየኖርን ነው፡፡ ሁናቴዎች ከሚያሳዩት ነገር ባሻገር አንድ ዘውግ ሌላውን ፈጽሞ የሚያጠፋው የእግዚአብሔር ፍቃድ ሲሆን ብቻ ይሆናል ብዬ አምናለሁ፡፡ ምናልባት የእኛ ሕይወት ለሩዋንዳ ድኅነት እንዲከፈል ግድ ብሎ ሊሆን ይችላል፡፡ ስለ አንድ ነገር እርግጠኛ ነኝ - እንደገና እንደምንገናኝ በአእምሮዬ ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ የለም፡፡
ከሀገሪቱ ለመውጣት ልሞክር ነው፣ ግን ይሳካልኝ አይሳካልኝ አላውቅም፡፡ በመንገድ ላይ ከገደሉኝ ስለ እኔ አትጨነቁ፤ በሚገባ ጸልያለሁ . . . ለሞትም ተዘጋጅቻለሁ፡፡ ከሩዋንዳ መውጣት ከቻልኩ ሰላም እንደተመለሰ ወዲያውኑ ሁላችሁንም አገኛችኋለሁ፡፡ የደረሰብኝን ሁሉ ቦን
ይነግራችኋል፡፡
የዳማሲን ጓደኛ ቦን በሌላ ጊዜ እንደነገረኝ ወንድሜ ደብዳቤውን እየጻፈ ሳለ እዚህ ሐሳብ ላይ ሲደርስ ዳማሲን ብዕሩን ቁጭ አድርጎ ቀና ብሎ እያየው ‹‹ቦን፣ ወዳጄ እንደሆንክ አውቃለሁ፤ ስሜቴም ሳይጎዳ እንዲቆይ ሞክረሃል፣ አሁን ልትነግረኝ የሚገባህ ሰዓት ላይ ነን - ከቤተሰቤ አባላት የተገደለ አለ እንዴ?›› ቦን ሁቱ ስለሆነ በዘር ጭፍጨፋው ወቅት በነጻነት ይጓጓዝና በአካባቢው ከቱትሲዎች ማንኛቸው እንደተገደሉ ያውቃል፡፡ የወላጆቼንና የቪያኒን ሞት ለራሱ በምስጢር የያዘው ለወንድሜ በጣም ስለሚጠነቀቅለትና ስሜቱን ሳይጎዳ ለመጠበቅ ስለፈለገ ነው፡፡
ዳማሲን በቀጥታ ሲጠይቀው ጊዜ ቦን ከባዱን መርዶ አረዳው፡፡ ጓደኛው የሚወዳቸው የቤተሰቡ አባላት ገና በሕይወት ያሉ እየመሰለው ደብዳቤውን መጻፉን እስኪጨርስ መጠበቅን አልፈለገም፡፡ ስለዚህ ቦን ለዳማሲን አባታችን፣ እናታችንና ታናሽ ወንድማችን እንደተገደሉና እኔ ምናልባት በሕይወት ተርፌ ሊሆን እንደሚችል ይነግረዋል፡፡ ዳማሲን ቀኑን ሙሉ ማለት ይቻላል አልቅሶ እንደነበር የደብዳቤው ቋሚ ምልክት የሆኑት የእንባ ጠብታዎች ይህንን ይመሰክራሉ፡፡
ዳማሲን ኪቩ ሐይቅን ለማቋረጥ ጀልባ ፍለጋ ከመሄዱ በፊት ደብዳቤውን እንደገና አውጥቶ አባባ፣ እማማና ቪያኒ በሚሉት ቃላት ግራና ቀኝ ቅንፎችን አስቀምጦ የሚከተሉትን አረፍተ ነገሮች አከለ፡፡ ኢማኪዩሌ እንድትጠነክሪ እለምንሻለሁ፡፡ እማማ፣ አባባና ቪያኒ መገደላቸውን አሁን ሰማሁ፡፡ በተቻለኝ ፍጥነት ላገኝሽ እሞክራለሁ፡፡ ራስሽን ሳሚልኝ፤ እቀፊልኝም! በጣም የሚወድሽ ወንድምሽ!
ይህ ካነበብኳቸው ነገሮች ሁሉ የሚሠቀጥጠው ነው፡፡ እንባ ባረጠባቸው ቃላት ላይ የጣቶቼን ጫፎች አላወስኳቸውና ይህንን ደብዳቤ ሳላለቅስ ማንበብ እንደማልችል ተረዳሁ፡፡
በኋላ ላይ እንደደረስኩበት ለዘላለም የኔ ጀግና ሆኖ የሚኖረው ቦን ወንድሜን በቤቱ ከቤተሰቡ ፍላጎት በተጻራሪ ሊሸሽገው ሞክሯል፡፡ በዘር ፍጅቱ የመጀመሪያ ቀናት ዳማሲንን በምስጢር ከአልጋው ስር በደኅና በመደበቅ ሊያቆየው ችሎ ነበር፡፡ የቦን ቤተሰብ ግን ያደረገውን ነገር ሲደርስበት ዳማሲንን ለገዳዮቹ እንዲሰጥ ግፊት ያሳድርበታል፡፡
ይባስ ብሎ ቱትሲ ልጆችን በዘውግ ስም ጥሪ ወቅት ማሸማቀቅ የሚወደው ቡሆሮ ከቦን አጎቶች አንዱ ነው፡፡ ቡሆሮ በሀገሪቱ ወስጥ ካሉ ጽንፈኛ ሁቱዎች ውስጥ አንዱ፣ መጥፎና አደገኛ ገዳይ ሆኖ ነበርና ሲጠራጠርበት ጊዜ ቦን ዳማሲንን በጭራሽ ቤት ውስጥ ማቆየት እንደሌለበት ይረዳል፡፡ አንድ ሌሊትም በጣም አምሽቶ በቤተሰቡ መሬት ራቅ ያለ ጥግ ላይ ጉድጓድ ቆፍሮ በዕንጨትና ቅጠላቅጠል ይሸፍነዋል፡፡ ገዳዮቹ በቡሆሮ ተጠቁመው ከመምጣታቸው በፊት ዳማሲንንም በጥንቃቄ ከመኝታ ክፍሉ ያስወጣና በጉድጓዱ ውስጥ ይደብቀዋል ፡፡
ዳማሲን በጉድጓድ ውስጥ ከሦስት ሳምንታት ለበለጠ ጊዜ ያህል ተደብቆ ሳለ ገዳዮቹ በቡሆሮ ውትወታ በተደጋጋሚ የቦንን ቤት አሠሡ፡፡ እነዚህ አራጆች ግን የማይሰለቹ በመሆናቸው የቦንን እያንዳንዷን እንቅስቃሴ ተከታትለው መጨረሻ ላይ ምግብ ወደ ውጪ ይዞ ሲሄድ ያዩታል፡፡ ሸሻጊው ጓደኛውና ተሸሻጊው ዳማሲን ገዳዮቹ ግቢውን ሊያስሱብን ይችላሉ ብለው ሠግተው ዳማሲን የኪቩ ሐይቅን ተሻግሮ ወደ ዛየር እንዲያቀና ይወስናሉ፡፡ (ቦን የቱትሲዎችን ሕይወት ለማትረፍ ሐይቁን የሚያሻግራቸውን አንድ ደግ ሳምራዊ ዐሳ አጥማጅ ሁቱ ያውቃል፡፡) ዳማሲንን ከጉድጓዱ አውጥቶ በየጥላው እየቆዩና ከጥሻ ጥሻ እየተሸጋገሩ ከእኩለ ሌሊት በኋላ ወደ ሐይቁ ሄዱ፡፡ መንገዱ ብዙ ጊዜ በመፍጀቱ ግን የዚያ ሌሊት ጀልባ ታመልጣቸዋለች፡፡
ነጋባቸው፡፡ በመሆኑም ዳማሲን ወደ ቦን ቤት ረጅም መንገድ ተጉዞ ተመልሶ አደጋ ላይ መውደቅን ስላልፈለገ ንሴንጄ በሚባል በሐይቁ አካባቢ የሚኖር የእርሱና የቦን ወዳጅ ቤት ቆየ፡፡ ንሴንጄ ቤተሰባችንን የሚወድ ለዘብተኛ ሁቱ ነው፡፡ አባቴ የብዙ ወንድሞቹን የትምህርት ክፍያ በመክፈል አግዟቸዋል፡፡ ስለሆነም ዳማሲንን ለዚያን ቀን መሸሸግ በመቻሉ ደስ ተሰኘ፡፡
የንሴንጄ ወንድም ሳይመን ግን የወንድሙን ያክል ቸር አልነበረም፡፡ ዳማሲንን በቤታቸው ሲደርስ በፈገግታና በወዳጅነት ተቀብሎታል … በማግስቱ ከሰዓት በኋላ ግን ወንድሜ በተኛበትና ንሴንጄም የጀልባ ጉዞውን ለማመቻቸት በወጣበት ሳይመን ከቤት ሾልኮ ወጥቶ የገዳዮቹን ቡድን ፈልጎ ዳማሲንን አሳልፎ ሰጠው፡፡
ከእራት በፊት ሳይመን ወንድሜን ቀስቅሶ ወደ ዛየር ከመሄድህ በፊት ልብሶችህን ልጠብልህ ይለዋል፡፡ ዳማሲንም ልብሶቹን ሁሉ አወላልቆ በውስጥ ልብስ ብቻ ይቀራል፡፡ ሳይመንም ልብሶቹን ይወስድበታል፡፡ (በኋላ ላይ እንደተናገረው ይህን ያደረገው ወንድሜን ከመሞቱ በፊት ለማሳፈርና ለማሸማቀቅ ፈልጎ ነው፡፡) ልብሶቹን ከወሰደበት በኋላም ሳይመን ወንድሜን በደርዘኖች የሚቆጠሩ ገዳዮች ይጠብቁት ወደነበረበት ወደ ዋናው ቤት ይጠራዋል፡፡ ወንድሜም ላይ ያለ ምኅረት ተረባረቡበት፤ እየደበደቡ ወደ መንገድ ጎተቱት፡፡ ከውስጥ ልብሱም ሌላ ምንም አልለበሰም፡፡ እኛ ቤት ትሠራ የነበረች አንድ ሴት ነገሩን ሁሉ አይታ የዳማሲንን የመጨረሻ ሰዓት ዝርዝር ሁኔታ ነግራኛለች፡፡ ‹‹ቆንጆዋ እህትህ የት ነች?›› ብለው ገዳዮቹ ወንድሜን ይጠይቁታል፡፡ ‹‹የት ነች ኢማኪዩሌ?›› በቤተሰብህ ያሉትን በረሮዎች አስከሬኖች አይተናቸዋል፤ እሷ ግን ገና አልተደረሰባትም… የት ነች? ንገረንና በነጻ እንለቅሃለን፤ ካልነገርከን ግን ሌሊቱን ሙሉ ስንከትፍህ እናድራለን፡፡ በል ኢማኪዩሌ የት እንዳለች ንገረንና በነጻ ትሰናበታለህ፡፡››
ፊቱ የተሰባበረውና ያባበጠው ዳማሲን የከበቡትን ገዳዮች አየት አድርጓቸው በሕይወቴ ሙሉ እንዳደረገልኝ ሁሉ በመጨረሻዋም ቅጽበት ለኔ ቆመልኝ
ቆንጆዋ እህቴ የት እንዳለች ባውቅ እንኳን አልነግራችሁም፡፡ ኢማኪዩሌን መቼም አታገኟትም… እናንተ ሁላችሁም ተደማምራችሁ ብትቀርቡ እንኳን በብልሃት አታህሏትም፡፡››
በገጀሮቻቸው እየመቱና እየወጋጉትም ‹‹እንዳንተ ብልህ ነች? አንተ ማስተርስ ዲግሪ እያለህ ያዝንህ፤ አልያዝንህም ወይ? አሁን እህትህ የት እንደተደበቀች ትነግረናለህ አትነግረንም!››
ዳማሲንም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ቀጥ ብሎ ቆመና ገዳዮቹ ላይ ሳቀባቸው፡፡ አለመፍራቱ ግራ አጋባቸው፤ ብዙ ቱትሲዎችን ገድለዋል፤ ሲገድሉም የተጠቂዎቻቸውን የአትግደሉኝ ተማጽኖ ማድመጥ ሲያረካቸው ቆይቷል፡፡ የዳማሲን መረጋጋት ደስታቸውን ነጠቃቸው፡፡
ከመደራደር ወይንም በወንድ ልጅ አምላክ እያለ ምህረታቸውን ከመለመን ይልቅ እንዲገድሉት ተገዳደራቸው፡፡ ‹ኑ›› አላቸው፡፡ ‹‹ምን ትጠብቃላችሁ? ዛሬ ወደ አምላኬ የምሄድባት ቀኔ ነች፡፡ በሁላችንም ዙሪያ አምላክ ይታየኛል፡፡ እያየ ነው፣ ወደ ቤቱ ሊወስደኝ እየጠበቀ፡፡ በሏ - ሥራችሁን ጨርሱና ወደ ገነት ላኩኛ፡፡ እንደ ሕፃናት የእቃ እቃ ጨዋታ አድርጋችሁት ሰውን ስትገድሉ ታሳዝኑኛላችሁ፡፡ ግድያ ጨዋታ አይደለም - አምላክን ካስቀየማችሁት አሁን ለተዝናናችሁበት ትከፍሉበታላችሁ፡፡ የምትቆራርጧቸው ንጹሃን ደም በፍርድ ቀን ይከተላችኋል፡፡ እኔ ግን ለእናንተ እየጸለይኩላችሁ ነው… የምትሰሩትን እርኩሰት እንድታዩና እጅግ ሳይዘገይባችሁ የአምላክን ይቅርታ እንድትጠይቁ እጸልይላችኋለሁ፡፡››
እነዚህ የወንድሜ የመጨረሻ ቃላት ናቸው፡፡ የግፍ ግድያውን ሕመም ምንም ባይቀንሰው በገዳዮቹ ፊት በጽናት መቆሙና ይዞት ከኖረው ክብር ጋር መሞቱ ያኮራኛል፡፡
አንደኛው የሳይመን ወንድም፣ ካሬራ የተባለው የወንጌላውያን ቄስ፣ ዳማሲን ሲናገር አላገጠበት፡፡ ‹‹ይህ ልጅ ራሱን እንደ ሰባኪ ቆጠረ እኮ፡፡ እዚህ ጋ ያለሁት ሰባኪ እኔ ብቻ ነኝ እንግዲህ፡፡ ግድያውንም ባርኬያለሁ፡፡ ይህችን ሀገር ከአንድ ተጨማሪ በረሮ በማጽዳታችሁ ባርኬያችኋለሁ›› ብሎ ገዳዮቹን አየት አድርጎ ‹‹ምን ትጠብቃላችሁ? ፈራችሁ እንዴ? አንድ በረሮ እንድትገድሉት ሲለማመጣችሁ ለምንድነው እሱ ጋ የምትገተሩት? ግደሉታ!›› ካሬራ ገዳዮቹን ወንጀል እንዲሰሩ አሸማቆ ገፋፋቸው፡፡
‹‹ቱትሲዎች ስትባሉ ከእኛ ከሁቱዎች በላይ እንደሆናችሁ ልታሳዩ ትሞክራላችሁ›› ብሎ አንዱ ገዳይ ጮኸና በዳማሲን ፊት ላይ ገጀራውን አነሳ፡፡ ‹‹ማስተርስ ዲግሪ ስላለህ በጣም የምትበልጠን ይመስልሃል? እስኪ ማስተርስ ዲግሪ ያለው ሰው አንጎል ምን እንደሚመስል ልየው!››
ገጀራውን በወንድሜ ራስ ላይ ሲሰነዝርበት ወንድሜ በጉልበቶቹ ወደቀ፡፡ ሌላ ገዳይም ወደፊት ተራምዶ መጥቶ ገጀራውን ሁለቴ ሰንዝሮ ሁለቱንም እጆቹን ገነጣጠላቸው፡፡ የመጀመሪያው ገዳይ ገጀራውን ሌላ ዙር ሰነዘረ - በዚህን ጊዜም የዳማሲንን የራስ ቅል ከፍቶ ወደ ውስጥ ለማየት ሞከረ፡፡ ከዚያም በወንድሜ ደም ተጨማልቆ መንደር ለመንደር እየዞረ በሰው ጭንቅላት ውስጥ የማስተርስ ዲግሪን እንዳየ ጉራውን ሲነፋ ዋለ፡፡
የዳማሲን ግድያ ዝርዝር ላይ አተኩሬ መቆዘምን ለራሴ አልፈቅድም፡፡ ሞትን እንዴት እንደተጋፈጣት፣ ከመሞቱ በፊት እንዴት ፈገግ እንዳለ፣ ብሎም ለገደሉት ሰዎች እንዴት እንደጸለየ ብቻ አስባለሁ፡፡ ዳማሲን የኔ ውድ የልብ ወዳጄና ጠንካራ ወንድሜ ነበር፡፡
በኋላ ላይ ከገዳዮቹ አንዱና የዳማሲን የትምህርት ቤት ጓደኛ ስለነበረው ሰማሄ ስለሚባል ሰው ወሬ ሰማሁ፡፡ ስሜቱን መቆጣጠር አቅቶት ተጎድቶ ለብዙ ቀናት አለቀሰ አሉ፡፡ ያለማቋረጥ ዳማሲንና እርሱ ስላደረጓቸው ነገሮች ሁሉ ያወሳል፡፡ እግር ኳስ መጫወት፣ በቡድን መንፈሳዊ መዝሙር መዘመርና ቤተ-ክርስቲያንን ማገልገል አይነቶቹን ትውስታዎቹን ይጠቃቅሳል፡፡ ለእርሱና ለሌሎች ልጆች ወንድሜ ያሳያቸው የነበረው ደግነት እየታወሰው በደለኝነት ተሰምቶታል፡፡ ሰማሄ ለሚያዳምጠው ሁሉ ጸጸቱን ይገልጻል፡፡
‹‹ከእንግዲህ አልገድልም›› ይላል፡፡ ‹‹የዳማሲንን ፊት ከአእምሮዬ በፍጹም አላወጣውም፡፡ ቃላቱ ልቤን ለዘላለም ሲያቃጥሉት ይኖራሉ፡፡ ይህን ዓይነት ልጅ መግደል ኃጢአት እኮ ነው፡፡››
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
በገጀሮቻቸው እየመቱና እየወጋጉትም ‹‹እንዳንተ ብልህ ነች? አንተ ማስተርስ ዲግሪ እያለህ ያዝንህ፤ አልያዝንህም ወይ? አሁን እህትህ የት እንደተደበቀች ትነግረናለህ አትነግረንም!››
ዳማሲንም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ቀጥ ብሎ ቆመና ገዳዮቹ ላይ ሳቀባቸው፡፡ አለመፍራቱ ግራ አጋባቸው፤ ብዙ ቱትሲዎችን ገድለዋል፤ ሲገድሉም የተጠቂዎቻቸውን የአትግደሉኝ ተማጽኖ ማድመጥ ሲያረካቸው ቆይቷል፡፡ የዳማሲን መረጋጋት ደስታቸውን ነጠቃቸው፡፡
ከመደራደር ወይንም በወንድ ልጅ አምላክ እያለ ምህረታቸውን ከመለመን ይልቅ እንዲገድሉት ተገዳደራቸው፡፡ ‹ኑ›› አላቸው፡፡ ‹‹ምን ትጠብቃላችሁ? ዛሬ ወደ አምላኬ የምሄድባት ቀኔ ነች፡፡ በሁላችንም ዙሪያ አምላክ ይታየኛል፡፡ እያየ ነው፣ ወደ ቤቱ ሊወስደኝ እየጠበቀ፡፡ በሏ - ሥራችሁን ጨርሱና ወደ ገነት ላኩኛ፡፡ እንደ ሕፃናት የእቃ እቃ ጨዋታ አድርጋችሁት ሰውን ስትገድሉ ታሳዝኑኛላችሁ፡፡ ግድያ ጨዋታ አይደለም - አምላክን ካስቀየማችሁት አሁን ለተዝናናችሁበት ትከፍሉበታላችሁ፡፡ የምትቆራርጧቸው ንጹሃን ደም በፍርድ ቀን ይከተላችኋል፡፡ እኔ ግን ለእናንተ እየጸለይኩላችሁ ነው… የምትሰሩትን እርኩሰት እንድታዩና እጅግ ሳይዘገይባችሁ የአምላክን ይቅርታ እንድትጠይቁ እጸልይላችኋለሁ፡፡››
እነዚህ የወንድሜ የመጨረሻ ቃላት ናቸው፡፡ የግፍ ግድያውን ሕመም ምንም ባይቀንሰው በገዳዮቹ ፊት በጽናት መቆሙና ይዞት ከኖረው ክብር ጋር መሞቱ ያኮራኛል፡፡
አንደኛው የሳይመን ወንድም፣ ካሬራ የተባለው የወንጌላውያን ቄስ፣ ዳማሲን ሲናገር አላገጠበት፡፡ ‹‹ይህ ልጅ ራሱን እንደ ሰባኪ ቆጠረ እኮ፡፡ እዚህ ጋ ያለሁት ሰባኪ እኔ ብቻ ነኝ እንግዲህ፡፡ ግድያውንም ባርኬያለሁ፡፡ ይህችን ሀገር ከአንድ ተጨማሪ በረሮ በማጽዳታችሁ ባርኬያችኋለሁ›› ብሎ ገዳዮቹን አየት አድርጎ ‹‹ምን ትጠብቃላችሁ? ፈራችሁ እንዴ? አንድ በረሮ እንድትገድሉት ሲለማመጣችሁ ለምንድነው እሱ ጋ የምትገተሩት? ግደሉታ!›› ካሬራ ገዳዮቹን ወንጀል እንዲሰሩ አሸማቆ ገፋፋቸው፡፡
‹‹ቱትሲዎች ስትባሉ ከእኛ ከሁቱዎች በላይ እንደሆናችሁ ልታሳዩ ትሞክራላችሁ›› ብሎ አንዱ ገዳይ ጮኸና በዳማሲን ፊት ላይ ገጀራውን አነሳ፡፡ ‹‹ማስተርስ ዲግሪ ስላለህ በጣም የምትበልጠን ይመስልሃል? እስኪ ማስተርስ ዲግሪ ያለው ሰው አንጎል ምን እንደሚመስል ልየው!››
ገጀራውን በወንድሜ ራስ ላይ ሲሰነዝርበት ወንድሜ በጉልበቶቹ ወደቀ፡፡ ሌላ ገዳይም ወደፊት ተራምዶ መጥቶ ገጀራውን ሁለቴ ሰንዝሮ ሁለቱንም እጆቹን ገነጣጠላቸው፡፡ የመጀመሪያው ገዳይ ገጀራውን ሌላ ዙር ሰነዘረ - በዚህን ጊዜም የዳማሲንን የራስ ቅል ከፍቶ ወደ ውስጥ ለማየት ሞከረ፡፡ ከዚያም በወንድሜ ደም ተጨማልቆ መንደር ለመንደር እየዞረ በሰው ጭንቅላት ውስጥ የማስተርስ ዲግሪን እንዳየ ጉራውን ሲነፋ ዋለ፡፡
የዳማሲን ግድያ ዝርዝር ላይ አተኩሬ መቆዘምን ለራሴ አልፈቅድም፡፡ ሞትን እንዴት እንደተጋፈጣት፣ ከመሞቱ በፊት እንዴት ፈገግ እንዳለ፣ ብሎም ለገደሉት ሰዎች እንዴት እንደጸለየ ብቻ አስባለሁ፡፡ ዳማሲን የኔ ውድ የልብ ወዳጄና ጠንካራ ወንድሜ ነበር፡፡
በኋላ ላይ ከገዳዮቹ አንዱና የዳማሲን የትምህርት ቤት ጓደኛ ስለነበረው ሰማሄ ስለሚባል ሰው ወሬ ሰማሁ፡፡ ስሜቱን መቆጣጠር አቅቶት ተጎድቶ ለብዙ ቀናት አለቀሰ አሉ፡፡ ያለማቋረጥ ዳማሲንና እርሱ ስላደረጓቸው ነገሮች ሁሉ ያወሳል፡፡ እግር ኳስ መጫወት፣ በቡድን መንፈሳዊ መዝሙር መዘመርና ቤተ-ክርስቲያንን ማገልገል አይነቶቹን ትውስታዎቹን ይጠቃቅሳል፡፡ ለእርሱና ለሌሎች ልጆች ወንድሜ ያሳያቸው የነበረው ደግነት እየታወሰው በደለኝነት ተሰምቶታል፡፡ ሰማሄ ለሚያዳምጠው ሁሉ ጸጸቱን ይገልጻል፡፡
‹‹ከእንግዲህ አልገድልም›› ይላል፡፡ ‹‹የዳማሲንን ፊት ከአእምሮዬ በፍጹም አላወጣውም፡፡ ቃላቱ ልቤን ለዘላለም ሲያቃጥሉት ይኖራሉ፡፡ ይህን ዓይነት ልጅ መግደል ኃጢአት እኮ ነው፡፡››
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍1
#የአመሻሽ_ፀፀት
፡
፡
#በኤፍሬም_ስዩም
፡
፡
በመስታወት አየ
በመስታወት ታየ።
በመስታወቱ ውስጥ ምስሉን እያየ ራሱን ጠየቀ፡፡ በአንደበቱና በመታወቂያው ላይ ዋሽቶ የሚናገረውንና ፅፎ ያስቀመጠውን
የእድሜውን ስፍራ ለራሱ መዋሸት አልቻለም፡፡ የደረሰበት የእድሜው መጠን ምን ማለት እንደሆነ የገባው ትላንትና
አምሽቶበት ከነበረው ግሮሰሪ ውስጥ የግሮሰሪው ባለቤት
እንደዘበት ጣል ባደረገው ንግግሩ ነበር፡፡
“እኔ ምልህ” አለው፡፡ ከባልኮኒው ኋላ ተቀምጦ የነበረው፡፡የግሮሰሪው ባለቤት፡፡
አምስት ደብል ጂን እስኪጠጣ ድረስ ከሰላምታ በቀር አንዳችም
ቃላት ሳይተነፍስ ለረዥም ሰአታት እርሡ ላይ ባልተለመደ ሁኔታ ወደ ፅሞና በሚጠጋ ጸጥታ ውስጥ ተቀምጦ የነበረው
የዚህ ቤትና የመጠጥ ደንበኛ...” አቤት ጠራኸኝ እንዴ? “አሉ:: እንደ መባነን ብሎ።
“አረጀህ እንዴ?” በድጋሚ የቤቱ ባለቤት፡፡ ሌላ ደንበኛው ያዘዘው
ብርጭቆ ውስጥ 'redlable' ወስኪ እየቀዱ፡፡
“እንዴት? እንደዛ ልትለኝ ቻልክ? ሽበትኩብህ ወይስ?”አላሥጨረሠውም፡፡ ለአይኑ ሀመም በታዘዘለት ትልቅ ነጭ መነፅር ውስጥ አተኩሮ ካየው በኋላ....” ዝምታ በጣም አበዛህ
ብዬ ነው፡፡” ባለ ግሮስሪው ይህንን ተናግሮ መቀመጫው ላይ
ሰውነቱን እያደላደለ የእጁን ሞባይል ይነካካ ገባ፡፡
እነሆ ከእነዚህ የቃላት ምልልሥ በኋላ በሁለቱ መሃል የነበረ ጭውውት ሲኖር “እሺ” “እሺ” የሚሉትና፡ “ምን አዲስ ነገር
አለ” የሚሉት ቃላት ብቻ ነበሩ፡፡
በመስታወት አየ
በመስታወት ታየ፡፡
አዲስ ነገር የለም ቀልቡም ከርሡ የለም
“አረጀህ እንዴ?” የሚለው ከትላንት ማታ እስከ አሁን ድረስ
ሕሊናውን ሊለቀው አልቻለም፡፡ ጥያቄውን ሽሽት ባልበደለው ሰው ላይ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ “ሁለተኛ እርሱ ቤት ሄጄ ብጠጣ
ሲል፡ ከውሳኔው በኋላ ወደ ቀልቡ ተመለስ
በእጁ መዳፍ ላይ ዘይት አፈሰሰ
መስታወት ፊት ቆሞ ሩቅ ወደ ኋላ በሃሳብ ፈሠሠ፡፡
ከጊዜያት በፊት አርግዛ የነበረች ፍቅረኛው አርግዣለሁ ስትለው
እርሱው በስጣት ብር ማስወረዷን አስታወሰ፡፡ በሰተረሳ ድርጊት
ተናደደ። በተረሳ ድርጊት በመጠን አበደ በተረሳ ድርጊት ተክዝ ብሉ ቆመ። በተረሳ
ድርጊት ሲጋራ ለኮስ፡፡ ለተረሳ ድርጊት መስታወት ፊት ላይ ጭሱን አፈሰሰ፡፡ በመስታወቱ ውስጥ የርሱን የማይመስል ድንግዝ ግዝ ፊት ታየው በሚያየው ድንግዝግዝ ፍርሀት ልቡን ገባው።
ነጭ የተስቀለ ፎጣ አወረደና መስታወቱን ወለወለ፡፡ በያዘው ሲጋራ
ምክንያት ደግሞ መስታወቱ ተመልሶ ጉም ለበሰ፡፡
ሲጋራውን ጥሎ በእግሩ ረግጦ አጠፋው መስታወቱን በድጋሚ ወልውሎ ወደ ተረሳው ነገር ተመለሰ።ተመለሰና እንዲህ አለ...
ይኼኔ ወልዳው ቢሆን ኖሮ የስንት አመት ልጅ ይኖረኝ ነበር።
የዘጠኝ አመት ልጅ ትኖረኝ (ይኖረኝ)ነበር” ራሡ መለሰ፡፡ ዘጠኝ
የሚለውን ቁጥር ተጠራጠረና ጣቶቹን እየነካካ በድጋሚ መቁጠር ጀመረ፡፡ “አንድ
አንድ አንድ
ሁለት
ሦስት
አራት አምስት ስድስት
ሰባት ስምንት..
ዘጠኝ አልተሣሳተም የዘጠኝ አመት ልጅ ይኖረው (ትኖረው) ነበር፡፡ በመስታወት አልፎ ወደ ሚገኘው ምስሉ ላይ አፈጠጠ
አሁን የአለበትን ሁኔታ ለመገመት
ልቡን ለመመዘን
ለመተንበይ ወደፊትን፡፡ አፈጠጠ፡፡ ምንም
አይነት መልስ ለማግኘት አልቻለም፡፡ እርሱ በደጅ የሚያገኛቸው ብዙዎቹ አብሮ እደጎቹ እና አብሮ ተማሮቹ ተለውጠዋል። ለእርሱ የሚታዩት
እጅግ በጣም ተለውጠው ነው፡፡ እነሱ ላይ የሚያየውን ለውጥ ግን እራሱ ላይ ሊያገኘው አልቻለም፡፡ በዚህም ምክንያት
በነበረበት የቀረ መስሎ ይሰማዋል፡፡ አንዳንዴ ግን የሚደነግጠው
በመንገድ ላይ አንዳንድ ህፃናቶች “ጋሼ? ሰዓት ስንት ነው?" ሲሉት ነው።
“አስር አመት ሞላው” የሚለው የጓደኛው ግጥም ምን ማለት
እንደሆነ ዘግይቶ ተረዳው፡፡ “አስር ዓመት ሞላው” ብሎ ለራሱ በለሆሳስ ከተናገረ በኋላ በቆመበት የሆነ አይነት ድርጊት
ማከናወን አማረው፡፡ ሊያከናውን የሚችላቸውን ነገሮች አብዝኞቹን አጠናቋል፡፡ከጥቂቶች በቀር
ጠዋት ይነሳል
ፊቱን ይታጠባል
ቁርስ የትም ይበላል
ወደ ሆኑ ሰዎች ስልኩን ይደውላል
ካፌ በረንዳ ላይ ጋዜጣ ያነባል።
በቃ፡፡ “ስራህ ምንድን ነው” ለሚሉት ሰዎች የሙሉ ጊዜ
ጸሐፊ ነኝ ብሎ ነው የሚያወራው፡፡ በየመጡት አዳዲስ ዓመቶች
ሁሉ በዚህ ክረምት ድንቅ የሆነ መፅሐፍ አበረክታለሁ በማለት
ምንም ምን ላይሰራ ጊዜዎች ነጉደዋል፡፡ ወይ ልብወለድ ሳይፅፍ፤ ወይ ልጅ ሳያሳቅፍ፡፡
ሃሳቡን መሸሽ ፈለገ
በሃሳቡ ግና በጣም ተፈለገ
መሸሽ አልቻለም በመስታወት ውስጥ ሚመለከተው ምስሉ ሁሉ ሳይቀር “ጊዜ” በሚል ርዕስ የተነደፈ ሃሳብ መስሎ ታየው፡፡
“ሴራው” በነበር የተጎነጎነ እንዲህ የተፃፈ..
የመጠሪያ ስም (ርእስ) = ሠ
የትምህረት ደረጃ = ያልጨረሰ
ዕድሜ = ያጋመሰ።
ከዚህ በላይ ታሪክ ከዚህ በላይ ልክ የሌለኝ ሰው ነኝ!! ብሎ እያሰላሰለ ሳለ ከኋላው አብራው ያደረችው ሴት ልጅ ጮክ ብላ ስትጠራው ተሰማውና “አቤት ጠራሽኝ እንዴ”
ሴቲቱ በማዘን እና በመገረም ስሜቶች መሃል በሆነ ሁኔታ “እንዴ ምን ማለትህ ነው ጠራሽኝ ትለኛለህ እንዴ? ስጠራህማ
ዘመን አለፈኝ እኮ፡፡ አሁንስ አረጀህ መሰለኝ” ብላ የጠራችበት
ምክንያት ስልኩ ደጋግሞ በመጥራቱ እደሆነ ነግራው ስልኩን አቀብላው ወደመጣችበት ተመለሰች፡፡
እርሱ ግን እስከዛሬ ድረስ በቆመበት ቀርቷል፡፡ መስታወት ፊት ለፊት ምስሉን እያየ፡፡
እና
በምስሉ እየታየ፡፡
💫አለቀ💫
፡
፡
#በኤፍሬም_ስዩም
፡
፡
በመስታወት አየ
በመስታወት ታየ።
በመስታወቱ ውስጥ ምስሉን እያየ ራሱን ጠየቀ፡፡ በአንደበቱና በመታወቂያው ላይ ዋሽቶ የሚናገረውንና ፅፎ ያስቀመጠውን
የእድሜውን ስፍራ ለራሱ መዋሸት አልቻለም፡፡ የደረሰበት የእድሜው መጠን ምን ማለት እንደሆነ የገባው ትላንትና
አምሽቶበት ከነበረው ግሮሰሪ ውስጥ የግሮሰሪው ባለቤት
እንደዘበት ጣል ባደረገው ንግግሩ ነበር፡፡
“እኔ ምልህ” አለው፡፡ ከባልኮኒው ኋላ ተቀምጦ የነበረው፡፡የግሮሰሪው ባለቤት፡፡
አምስት ደብል ጂን እስኪጠጣ ድረስ ከሰላምታ በቀር አንዳችም
ቃላት ሳይተነፍስ ለረዥም ሰአታት እርሡ ላይ ባልተለመደ ሁኔታ ወደ ፅሞና በሚጠጋ ጸጥታ ውስጥ ተቀምጦ የነበረው
የዚህ ቤትና የመጠጥ ደንበኛ...” አቤት ጠራኸኝ እንዴ? “አሉ:: እንደ መባነን ብሎ።
“አረጀህ እንዴ?” በድጋሚ የቤቱ ባለቤት፡፡ ሌላ ደንበኛው ያዘዘው
ብርጭቆ ውስጥ 'redlable' ወስኪ እየቀዱ፡፡
“እንዴት? እንደዛ ልትለኝ ቻልክ? ሽበትኩብህ ወይስ?”አላሥጨረሠውም፡፡ ለአይኑ ሀመም በታዘዘለት ትልቅ ነጭ መነፅር ውስጥ አተኩሮ ካየው በኋላ....” ዝምታ በጣም አበዛህ
ብዬ ነው፡፡” ባለ ግሮስሪው ይህንን ተናግሮ መቀመጫው ላይ
ሰውነቱን እያደላደለ የእጁን ሞባይል ይነካካ ገባ፡፡
እነሆ ከእነዚህ የቃላት ምልልሥ በኋላ በሁለቱ መሃል የነበረ ጭውውት ሲኖር “እሺ” “እሺ” የሚሉትና፡ “ምን አዲስ ነገር
አለ” የሚሉት ቃላት ብቻ ነበሩ፡፡
በመስታወት አየ
በመስታወት ታየ፡፡
አዲስ ነገር የለም ቀልቡም ከርሡ የለም
“አረጀህ እንዴ?” የሚለው ከትላንት ማታ እስከ አሁን ድረስ
ሕሊናውን ሊለቀው አልቻለም፡፡ ጥያቄውን ሽሽት ባልበደለው ሰው ላይ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ “ሁለተኛ እርሱ ቤት ሄጄ ብጠጣ
ሲል፡ ከውሳኔው በኋላ ወደ ቀልቡ ተመለስ
በእጁ መዳፍ ላይ ዘይት አፈሰሰ
መስታወት ፊት ቆሞ ሩቅ ወደ ኋላ በሃሳብ ፈሠሠ፡፡
ከጊዜያት በፊት አርግዛ የነበረች ፍቅረኛው አርግዣለሁ ስትለው
እርሱው በስጣት ብር ማስወረዷን አስታወሰ፡፡ በሰተረሳ ድርጊት
ተናደደ። በተረሳ ድርጊት በመጠን አበደ በተረሳ ድርጊት ተክዝ ብሉ ቆመ። በተረሳ
ድርጊት ሲጋራ ለኮስ፡፡ ለተረሳ ድርጊት መስታወት ፊት ላይ ጭሱን አፈሰሰ፡፡ በመስታወቱ ውስጥ የርሱን የማይመስል ድንግዝ ግዝ ፊት ታየው በሚያየው ድንግዝግዝ ፍርሀት ልቡን ገባው።
ነጭ የተስቀለ ፎጣ አወረደና መስታወቱን ወለወለ፡፡ በያዘው ሲጋራ
ምክንያት ደግሞ መስታወቱ ተመልሶ ጉም ለበሰ፡፡
ሲጋራውን ጥሎ በእግሩ ረግጦ አጠፋው መስታወቱን በድጋሚ ወልውሎ ወደ ተረሳው ነገር ተመለሰ።ተመለሰና እንዲህ አለ...
ይኼኔ ወልዳው ቢሆን ኖሮ የስንት አመት ልጅ ይኖረኝ ነበር።
የዘጠኝ አመት ልጅ ትኖረኝ (ይኖረኝ)ነበር” ራሡ መለሰ፡፡ ዘጠኝ
የሚለውን ቁጥር ተጠራጠረና ጣቶቹን እየነካካ በድጋሚ መቁጠር ጀመረ፡፡ “አንድ
አንድ አንድ
ሁለት
ሦስት
አራት አምስት ስድስት
ሰባት ስምንት..
ዘጠኝ አልተሣሳተም የዘጠኝ አመት ልጅ ይኖረው (ትኖረው) ነበር፡፡ በመስታወት አልፎ ወደ ሚገኘው ምስሉ ላይ አፈጠጠ
አሁን የአለበትን ሁኔታ ለመገመት
ልቡን ለመመዘን
ለመተንበይ ወደፊትን፡፡ አፈጠጠ፡፡ ምንም
አይነት መልስ ለማግኘት አልቻለም፡፡ እርሱ በደጅ የሚያገኛቸው ብዙዎቹ አብሮ እደጎቹ እና አብሮ ተማሮቹ ተለውጠዋል። ለእርሱ የሚታዩት
እጅግ በጣም ተለውጠው ነው፡፡ እነሱ ላይ የሚያየውን ለውጥ ግን እራሱ ላይ ሊያገኘው አልቻለም፡፡ በዚህም ምክንያት
በነበረበት የቀረ መስሎ ይሰማዋል፡፡ አንዳንዴ ግን የሚደነግጠው
በመንገድ ላይ አንዳንድ ህፃናቶች “ጋሼ? ሰዓት ስንት ነው?" ሲሉት ነው።
“አስር አመት ሞላው” የሚለው የጓደኛው ግጥም ምን ማለት
እንደሆነ ዘግይቶ ተረዳው፡፡ “አስር ዓመት ሞላው” ብሎ ለራሱ በለሆሳስ ከተናገረ በኋላ በቆመበት የሆነ አይነት ድርጊት
ማከናወን አማረው፡፡ ሊያከናውን የሚችላቸውን ነገሮች አብዝኞቹን አጠናቋል፡፡ከጥቂቶች በቀር
ጠዋት ይነሳል
ፊቱን ይታጠባል
ቁርስ የትም ይበላል
ወደ ሆኑ ሰዎች ስልኩን ይደውላል
ካፌ በረንዳ ላይ ጋዜጣ ያነባል።
በቃ፡፡ “ስራህ ምንድን ነው” ለሚሉት ሰዎች የሙሉ ጊዜ
ጸሐፊ ነኝ ብሎ ነው የሚያወራው፡፡ በየመጡት አዳዲስ ዓመቶች
ሁሉ በዚህ ክረምት ድንቅ የሆነ መፅሐፍ አበረክታለሁ በማለት
ምንም ምን ላይሰራ ጊዜዎች ነጉደዋል፡፡ ወይ ልብወለድ ሳይፅፍ፤ ወይ ልጅ ሳያሳቅፍ፡፡
ሃሳቡን መሸሽ ፈለገ
በሃሳቡ ግና በጣም ተፈለገ
መሸሽ አልቻለም በመስታወት ውስጥ ሚመለከተው ምስሉ ሁሉ ሳይቀር “ጊዜ” በሚል ርዕስ የተነደፈ ሃሳብ መስሎ ታየው፡፡
“ሴራው” በነበር የተጎነጎነ እንዲህ የተፃፈ..
የመጠሪያ ስም (ርእስ) = ሠ
የትምህረት ደረጃ = ያልጨረሰ
ዕድሜ = ያጋመሰ።
ከዚህ በላይ ታሪክ ከዚህ በላይ ልክ የሌለኝ ሰው ነኝ!! ብሎ እያሰላሰለ ሳለ ከኋላው አብራው ያደረችው ሴት ልጅ ጮክ ብላ ስትጠራው ተሰማውና “አቤት ጠራሽኝ እንዴ”
ሴቲቱ በማዘን እና በመገረም ስሜቶች መሃል በሆነ ሁኔታ “እንዴ ምን ማለትህ ነው ጠራሽኝ ትለኛለህ እንዴ? ስጠራህማ
ዘመን አለፈኝ እኮ፡፡ አሁንስ አረጀህ መሰለኝ” ብላ የጠራችበት
ምክንያት ስልኩ ደጋግሞ በመጥራቱ እደሆነ ነግራው ስልኩን አቀብላው ወደመጣችበት ተመለሰች፡፡
እርሱ ግን እስከዛሬ ድረስ በቆመበት ቀርቷል፡፡ መስታወት ፊት ለፊት ምስሉን እያየ፡፡
እና
በምስሉ እየታየ፡፡
💫አለቀ💫
👍2
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#የስደተኞች_መጠለያው_ምቾት
፡
፡
የፈረንሳዮቹ የስደተኞች መጠለያ የታጠቁ ወታደሮች የሚጠብቁት፣ ለቱትሲዎች ከለላ የሚሰጥና ሁቱዎችን የሚያገል ስፍራ ነው፡፡ ወታደሮቹ ስምንት ታንክ-መሰል ብረትለበስ ተሸከርካሪዎችን በግማሽ ክብ ቅርጽ ከትምህርት ቤቱ ሕንጻዎች ፊት ለፊት ያቆሙ ሲሆን የምሽጉን ውጨኛውን ክፍል ደግሞ ቀን ከሌት ቢያንስ መቶ የሚሆኑ ወታደሮች ይቃኙታል፡፡ እኛም ብረት-ለበስ ተሸከርካሪዎች ባሉበት ግማሽ ክብ ውስጥ ሙሉ ጊዜ ሰጥተው እንዲከላከሉንና መጸዳዳት ስንፈልግም ወደ ጫካ እንዲወስዱን ከተመደቡ ሰላሳ ወታደሮች ጋር እንኖራለን፡፡
የፈረንሳይ ወታደሮች በተደጋጋሚ ስለምንኖርበት ሁኔታ ይቅርታ ሲጠይቁን ያስቁኛል፡፡ ከመጣንበት ጋር ሲነጻጸር ፍጹም የምቾት ሕይወት በመኖር ላይ ነን፡፡ መጀመሪያ ላይ ከምንጭ ውሃ እናግዝና ገላችንንና ልብሳችንን በሳሙና እናጥብ ነበር!
ውጪ ላይ መተኛታችንን ፈረንሳውያኑ ወታደሮች እንደ ዋና መከራ ቢያዩትም እኛ ግን በደስታ ተቀብለነዋል፡፡ ብዙውን ጊዜ በቆሻሻና በዛፍ ቅጠላ ቅጠል ተሸፍኜ በአለትና ድንጋይ ላይ በመተኛቴ የተነሳ እያመመኝ ብነሳም ክዋክብት ላይ አንጋጥጬ መተኛቱን ወድጄዋለሁ፡፡ የእግዚአብሔርን ፊት በቀኑ መጀመሪያ ላይ የማየት ያህል ነው፡፡
ምግብ እንድናዘጋጅ አይፈቀድልንም፡፡ ይህ የሆነው ትኩስ ምግብ ስላልነበራቸው ሲሆን አለማዘጋጀታችንም ለእኛ ምንም ችግር አያመጣም፡፡ ወታደሮቹ የታሸገ አይብ፣ ጣፋጭ ኮቸሮ፣ እሽግ የዱቄት ወተትና ፍራፍሬ ይመግቡናል፡፡ የምመገበው የተወሰነ ምግብ ቢሆንም ቀስ በቀስ ሰውነቴ እየጨመረ ሄደ፤ ወገቤም ወደ ውስጥ መግባቱን አቆመ፡፡
ፈረንሳውያን ሥራቸው እኛን መከላከል መሆኑን ይናገራሉ፡፡ ይህንን ተግባራቸውንም በሚገባ ተወጥተውታል፡፡ በምሽጉ ውስጥ በቆየሁበት ወቅት አንድም ጊዜ እንኳን በገዳዮቹ ማስፈራሪያ ደርሶብኝ አያውቅም፡፡ ሆኖም ግን ሁቱዎች ብዙውን ጊዜ በውጪው የምሽጉ ክፍል በመሰብሰብ በተደረደሩት ተሸከርካሪዎች መካከል እኛን ለማየት ይሞክራሉ፡፡ በእንስሳት መጠበቂያ ያለን እንስሶች እንደሆንን ሁሉ ያፈጡብናል … ከመጥፋት ጠርዝ ድረስ የታደነ ዘውግ ብቸኛ ቅሪቶች፡፡
‹‹እንስሳት እንደሆናችሁ ሁሉ ያዩዋችኋል፣ ግን እነርሱ ናቸው እንስሶቹ›› አለኝ የወታደሮቹ አበጋዝ አንድ ቀን ጠዋት ከደረስኩ ከጥቂት ጊዜ በኋላ፡፡ ፈረንሳይኛ በጥሩ ሁኔታ እንደምችል ስለተረዳ ብዙ አዋራኝ፡፡ ታሪኬን ነገርኩት፤ በጣም እንዳዘነልኝም ታየኝ፡፡ በሩዋንዳ ቱትሲዎች ያሳለፉትን፣ ታሪካችንንና የዘውግ ግጭቶችን ጣጣ ሁሉ ያውቃል፡፡
‹‹ባንቺና በኔ መካከል የሚቀር ነገር ልንገርሽ፤ የሀገሬ የርዕሰ-ብሔር ከራሱ ጋር አንዴት መታረቅ እንደሚችል አላውቅም - ጸጸቱ እንደማይገድለው›› አለኝ፡፡ ‹‹ብዙ ሁቱዎችን እንዴት ሰው እንደሚገድሉ ስላሠለጠነች ፈረንሳይ በእጆቿ ላይ ደም አለባት፡፡››
በሩዋንዳ ለተከሰተው ነገር የውጪ ዜጋ ወቀሳውን ሲቀበል ስሰማ ይህ የመጀመሪያዬ ነው፡፡ በመሆኑም ይህ ለነፍሴ ጥሩ ነገር አደረገላት፡፡ ዓለም እየደረሰብን ያለውን ነገር አይቶ ለመርሳት መምረጡን በማወቄ የቄሱን ሬድዮ ስሰማ ብዙ ጊዜ ተስፋ እቆርጥ ነበር፡፡
‹‹ይህን ያህል ስለተረዳኸኝ አመሰግናለሁ›› ስል መለስኩለት፡፡ ‹‹ይህን እያደረጉ ያሉት ሰዎች በጣም መጥፎዎች ናቸው፡፡
‹‹መጥፎ? መጥፎ! ኢማኪዩሌ ከንቱ ግፈኞች ናቸው፡፡ ጭራቆች ናቸው! በደኅና ሁናቴ ላይ እንዳለሽ እንድታውቂ እፈልጋለሁ፡፡ እኔ እዚህ በሥራ ላይ እያለሁ አንዳች ጉዳት አይመጣብሽም›› አለኝ በወገቡ ላይ ያገነደረውን ጠመንጃ መታ መታ እያደረገ፡፡ ‹‹ላንቺ ከመከላከልም በላይ አደርግልሻለሁ፡፡ የተወሰነ ፍትሕም እለግስሻለሁ፡፡ አሁንም ይህ በኔና ባንቺ መካከል ይቅር እንጂ በቀል ከፈለግሽ ያንቺው ድርሻ ነው፡፡ ይፈልጉሽ የነበሩትን ወይንም ወላጆችሽንና ወንድሞችሽን የገደሉትን ሁቱዎች ስሞች ብትሰጭኝ አስገድልልሻለሁ፡፡
ያቀረበው ሐሳብ አስደነገጠኝ፡፡ በመታጠቢያ ቤቱ በነበርኩባቸው የመጀመሪያ ቀናት ሰሞን የተመኘሁት ይህንኑ ነበር፡፡ በኛ ሰዎች ላይ እየተፈጸሙ የነበሩትን ግድያዎች ቄሱ በነገሩን ጊዜ በቀልን በጽኑ በመፈለጌ ሁቱዎችን የምገድልበት ጠመንጃና መድፍ ቢኖረኝ ተመኝቼ ነበር፡፡ ያ ግን ልቤን ለእግዚአብሔር ምኅረት ከመክፈቴና ከገዳዮቹ ጋር ሰላም ከመፍጠሬ በፊት ነው፡፡
መኰንኑ ያቀረበልኝ ትክክለኛውን በቀል ነው - በኔ ትዕዛዝ የሚገድሉ የሠለጠኑና የታጠቁ ወታደሮችን፡፡ ማድረግ የሚጠበቅብኝ ብቸኛው ነገር አንድ ስም ሹክ ማለትና የቤተሰቤንና በሺዎች የሚቆጠሩትን በየጎዳናው እየበሰበሱ የነበሩትን ሰዎች ደም መበቀል ነው፡፡ በቀሉ ከልቡ የመጣ ቢሆንም በመኰንኑ ድምጽ ውስጥ ዲያብሎስ ይሰማኛል፡፡ በወቅቱ የምፈልገው ብቸኛ ነገር ሰላም ሆኖ ሳለ ይህ መኰንን በግድያ ቃል ኪዳኖች ይፈታተነኛል፡፡ እጄን ወደ ኪሴ አስገብቼ በአባቴ መቁጠሪያ
ጠቀለልኩት፡፡ ‹‹ይህን አደርግልሻለሁ በማለትህ አመሰግናለሁ -››
‹‹የምትፈልጊውን እገድልለሻለሁ!›› ለመግደል በጣም ከመጓጓቱ የተነሣ ንግግሬን እንኳን አላስጨርስ አለኝ፡፡ ‹‹በዚህ ምሽግ የምታውቂው ሁቱ ካለ ንገሪኝና እኔ ራሴ እገድለዋለሁ፡፡ ሁሉንም እጠላቸዋለሁ፡፡››
‹‹አዎን፣ እነዚህ ገዳዮች እንጂ ሁቱዎች ሁሉ ከንቱ አይደሉም መኰንን ሆይ፡፡ በዲያብሎስ ተታለዋል… ከአምላክ ርቀው ሄደዋል እና -››
‹‹ኢማኪዩሌ ሁቱዎች ከንቱ ናቸው›› እንደገና አቋረጠኝ፡፡ ‹‹ያደረጉት ከንቱ ነው፡፡ ይህ የጌታ ፈቃድ አሊያም የዲያብሎስ ሥራ እንደሆነ አትንገሪኝ - የሁቱዎች ሥራ ነው፡፡ እናም ብድራቸውን ያገኟታል፡፡ ሐሳብሽን ከቀየርሽ አሳውቂኝ፡፡ ለሌላ ሰው እኮ ልግደል አልልም፤ ታውቂያለሽ፡፡››
አምላክ የመኰንኑን ልብ በምህረቱ እንዲነካ ጸልዬ ለገዳዮቹም እንደገና ገጀራዎቻቸውን እንዲጥሉና የእግዚአብሔርን ምኅረት እንዲለምኑ ጸለይኩ፡፡ የመኰንኑ ንዴት በሩዋንዳ የጥላቻና ያለመተማመኑ ዑደት በቀላሉ እንደማይሰበር እንዳስብ አደረገኝ፡፡ እንዲያውም ግድያው ካቆመም በኋላ በእርግጠኝነት የባሰ መራር ሁኔታ ሊኖር ይችላል፤ ወደ ባሰ ሽብር የሚፈነዳ መራርነት፡፡ የእግዚአብሔር መለኮታዊ ምኅረት ብቻ ያንን አሁን ከመከሰት ያቆመው ይሆናል፡፡ በምንም ዓይነት መንገድ አምላክ ቢያስቀምጠኝ ያንን ማየት እችላለሁ - ሌሎች እንዲኖሩ ማድረግም የሕይወቴ ሥራ ዋነኛ ክፍል ይሆናል፡፡
በቀጣዩ ቀን መኰንኑ ቃሉን መጠበቁን አሳየ - ሁቱዎችን በእውነት ይጠላ ኖሯል፡፡ አንድ እየደማ ያለና ‹‹የዘር ጭፍጨፋ ተራፊ ነኝ፤ የቆሰልኩትም ከቱትሲ አማጽያን ጎን ስዋጋ ነው›› የሚል ሰው ወደ ምሽጉ ገብቶ ይዘዋወራል፡፡ መኰንኑ ግን ስላላመነው ወታደሮቹ አንበርክከውና ጠመንጃዎቻቸውን ራሱ ላይ ደግነው እንዲጠይቁት አደረገ፡፡ መጀመሪያ ላይ ሲጠይቁት የኢንተርሃምዌ አባል መሆኑን ካደ፡፡ ከብዙ ምርመራ በኋላ ግን ተስፋ ቆረጠና ተናዘዘ፡፡ መኰንኑም ለወታደሮቹ ራሱን ሲነቀንቅላቸው ጎትተው ወሰዱት፤ ከዚያ በኋላም በጭራሽ አላየነውም፡፡ ከወታደሮቹ አንደኛው በሌላ ጊዜ ሰውዬው የኢንተርሃምዌ ሰላይ እንደሆነ ማመኑን ነገረኝ፡፡
‹‹ስለሱ አትጨነቂ - ከአሁን በኋላ አያስቸግርሽም›› አለኝ፡፡
ለአክስቶቼና ለልጆቻቸው
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#የስደተኞች_መጠለያው_ምቾት
፡
፡
የፈረንሳዮቹ የስደተኞች መጠለያ የታጠቁ ወታደሮች የሚጠብቁት፣ ለቱትሲዎች ከለላ የሚሰጥና ሁቱዎችን የሚያገል ስፍራ ነው፡፡ ወታደሮቹ ስምንት ታንክ-መሰል ብረትለበስ ተሸከርካሪዎችን በግማሽ ክብ ቅርጽ ከትምህርት ቤቱ ሕንጻዎች ፊት ለፊት ያቆሙ ሲሆን የምሽጉን ውጨኛውን ክፍል ደግሞ ቀን ከሌት ቢያንስ መቶ የሚሆኑ ወታደሮች ይቃኙታል፡፡ እኛም ብረት-ለበስ ተሸከርካሪዎች ባሉበት ግማሽ ክብ ውስጥ ሙሉ ጊዜ ሰጥተው እንዲከላከሉንና መጸዳዳት ስንፈልግም ወደ ጫካ እንዲወስዱን ከተመደቡ ሰላሳ ወታደሮች ጋር እንኖራለን፡፡
የፈረንሳይ ወታደሮች በተደጋጋሚ ስለምንኖርበት ሁኔታ ይቅርታ ሲጠይቁን ያስቁኛል፡፡ ከመጣንበት ጋር ሲነጻጸር ፍጹም የምቾት ሕይወት በመኖር ላይ ነን፡፡ መጀመሪያ ላይ ከምንጭ ውሃ እናግዝና ገላችንንና ልብሳችንን በሳሙና እናጥብ ነበር!
ውጪ ላይ መተኛታችንን ፈረንሳውያኑ ወታደሮች እንደ ዋና መከራ ቢያዩትም እኛ ግን በደስታ ተቀብለነዋል፡፡ ብዙውን ጊዜ በቆሻሻና በዛፍ ቅጠላ ቅጠል ተሸፍኜ በአለትና ድንጋይ ላይ በመተኛቴ የተነሳ እያመመኝ ብነሳም ክዋክብት ላይ አንጋጥጬ መተኛቱን ወድጄዋለሁ፡፡ የእግዚአብሔርን ፊት በቀኑ መጀመሪያ ላይ የማየት ያህል ነው፡፡
ምግብ እንድናዘጋጅ አይፈቀድልንም፡፡ ይህ የሆነው ትኩስ ምግብ ስላልነበራቸው ሲሆን አለማዘጋጀታችንም ለእኛ ምንም ችግር አያመጣም፡፡ ወታደሮቹ የታሸገ አይብ፣ ጣፋጭ ኮቸሮ፣ እሽግ የዱቄት ወተትና ፍራፍሬ ይመግቡናል፡፡ የምመገበው የተወሰነ ምግብ ቢሆንም ቀስ በቀስ ሰውነቴ እየጨመረ ሄደ፤ ወገቤም ወደ ውስጥ መግባቱን አቆመ፡፡
ፈረንሳውያን ሥራቸው እኛን መከላከል መሆኑን ይናገራሉ፡፡ ይህንን ተግባራቸውንም በሚገባ ተወጥተውታል፡፡ በምሽጉ ውስጥ በቆየሁበት ወቅት አንድም ጊዜ እንኳን በገዳዮቹ ማስፈራሪያ ደርሶብኝ አያውቅም፡፡ ሆኖም ግን ሁቱዎች ብዙውን ጊዜ በውጪው የምሽጉ ክፍል በመሰብሰብ በተደረደሩት ተሸከርካሪዎች መካከል እኛን ለማየት ይሞክራሉ፡፡ በእንስሳት መጠበቂያ ያለን እንስሶች እንደሆንን ሁሉ ያፈጡብናል … ከመጥፋት ጠርዝ ድረስ የታደነ ዘውግ ብቸኛ ቅሪቶች፡፡
‹‹እንስሳት እንደሆናችሁ ሁሉ ያዩዋችኋል፣ ግን እነርሱ ናቸው እንስሶቹ›› አለኝ የወታደሮቹ አበጋዝ አንድ ቀን ጠዋት ከደረስኩ ከጥቂት ጊዜ በኋላ፡፡ ፈረንሳይኛ በጥሩ ሁኔታ እንደምችል ስለተረዳ ብዙ አዋራኝ፡፡ ታሪኬን ነገርኩት፤ በጣም እንዳዘነልኝም ታየኝ፡፡ በሩዋንዳ ቱትሲዎች ያሳለፉትን፣ ታሪካችንንና የዘውግ ግጭቶችን ጣጣ ሁሉ ያውቃል፡፡
‹‹ባንቺና በኔ መካከል የሚቀር ነገር ልንገርሽ፤ የሀገሬ የርዕሰ-ብሔር ከራሱ ጋር አንዴት መታረቅ እንደሚችል አላውቅም - ጸጸቱ እንደማይገድለው›› አለኝ፡፡ ‹‹ብዙ ሁቱዎችን እንዴት ሰው እንደሚገድሉ ስላሠለጠነች ፈረንሳይ በእጆቿ ላይ ደም አለባት፡፡››
በሩዋንዳ ለተከሰተው ነገር የውጪ ዜጋ ወቀሳውን ሲቀበል ስሰማ ይህ የመጀመሪያዬ ነው፡፡ በመሆኑም ይህ ለነፍሴ ጥሩ ነገር አደረገላት፡፡ ዓለም እየደረሰብን ያለውን ነገር አይቶ ለመርሳት መምረጡን በማወቄ የቄሱን ሬድዮ ስሰማ ብዙ ጊዜ ተስፋ እቆርጥ ነበር፡፡
‹‹ይህን ያህል ስለተረዳኸኝ አመሰግናለሁ›› ስል መለስኩለት፡፡ ‹‹ይህን እያደረጉ ያሉት ሰዎች በጣም መጥፎዎች ናቸው፡፡
‹‹መጥፎ? መጥፎ! ኢማኪዩሌ ከንቱ ግፈኞች ናቸው፡፡ ጭራቆች ናቸው! በደኅና ሁናቴ ላይ እንዳለሽ እንድታውቂ እፈልጋለሁ፡፡ እኔ እዚህ በሥራ ላይ እያለሁ አንዳች ጉዳት አይመጣብሽም›› አለኝ በወገቡ ላይ ያገነደረውን ጠመንጃ መታ መታ እያደረገ፡፡ ‹‹ላንቺ ከመከላከልም በላይ አደርግልሻለሁ፡፡ የተወሰነ ፍትሕም እለግስሻለሁ፡፡ አሁንም ይህ በኔና ባንቺ መካከል ይቅር እንጂ በቀል ከፈለግሽ ያንቺው ድርሻ ነው፡፡ ይፈልጉሽ የነበሩትን ወይንም ወላጆችሽንና ወንድሞችሽን የገደሉትን ሁቱዎች ስሞች ብትሰጭኝ አስገድልልሻለሁ፡፡
ያቀረበው ሐሳብ አስደነገጠኝ፡፡ በመታጠቢያ ቤቱ በነበርኩባቸው የመጀመሪያ ቀናት ሰሞን የተመኘሁት ይህንኑ ነበር፡፡ በኛ ሰዎች ላይ እየተፈጸሙ የነበሩትን ግድያዎች ቄሱ በነገሩን ጊዜ በቀልን በጽኑ በመፈለጌ ሁቱዎችን የምገድልበት ጠመንጃና መድፍ ቢኖረኝ ተመኝቼ ነበር፡፡ ያ ግን ልቤን ለእግዚአብሔር ምኅረት ከመክፈቴና ከገዳዮቹ ጋር ሰላም ከመፍጠሬ በፊት ነው፡፡
መኰንኑ ያቀረበልኝ ትክክለኛውን በቀል ነው - በኔ ትዕዛዝ የሚገድሉ የሠለጠኑና የታጠቁ ወታደሮችን፡፡ ማድረግ የሚጠበቅብኝ ብቸኛው ነገር አንድ ስም ሹክ ማለትና የቤተሰቤንና በሺዎች የሚቆጠሩትን በየጎዳናው እየበሰበሱ የነበሩትን ሰዎች ደም መበቀል ነው፡፡ በቀሉ ከልቡ የመጣ ቢሆንም በመኰንኑ ድምጽ ውስጥ ዲያብሎስ ይሰማኛል፡፡ በወቅቱ የምፈልገው ብቸኛ ነገር ሰላም ሆኖ ሳለ ይህ መኰንን በግድያ ቃል ኪዳኖች ይፈታተነኛል፡፡ እጄን ወደ ኪሴ አስገብቼ በአባቴ መቁጠሪያ
ጠቀለልኩት፡፡ ‹‹ይህን አደርግልሻለሁ በማለትህ አመሰግናለሁ -››
‹‹የምትፈልጊውን እገድልለሻለሁ!›› ለመግደል በጣም ከመጓጓቱ የተነሣ ንግግሬን እንኳን አላስጨርስ አለኝ፡፡ ‹‹በዚህ ምሽግ የምታውቂው ሁቱ ካለ ንገሪኝና እኔ ራሴ እገድለዋለሁ፡፡ ሁሉንም እጠላቸዋለሁ፡፡››
‹‹አዎን፣ እነዚህ ገዳዮች እንጂ ሁቱዎች ሁሉ ከንቱ አይደሉም መኰንን ሆይ፡፡ በዲያብሎስ ተታለዋል… ከአምላክ ርቀው ሄደዋል እና -››
‹‹ኢማኪዩሌ ሁቱዎች ከንቱ ናቸው›› እንደገና አቋረጠኝ፡፡ ‹‹ያደረጉት ከንቱ ነው፡፡ ይህ የጌታ ፈቃድ አሊያም የዲያብሎስ ሥራ እንደሆነ አትንገሪኝ - የሁቱዎች ሥራ ነው፡፡ እናም ብድራቸውን ያገኟታል፡፡ ሐሳብሽን ከቀየርሽ አሳውቂኝ፡፡ ለሌላ ሰው እኮ ልግደል አልልም፤ ታውቂያለሽ፡፡››
አምላክ የመኰንኑን ልብ በምህረቱ እንዲነካ ጸልዬ ለገዳዮቹም እንደገና ገጀራዎቻቸውን እንዲጥሉና የእግዚአብሔርን ምኅረት እንዲለምኑ ጸለይኩ፡፡ የመኰንኑ ንዴት በሩዋንዳ የጥላቻና ያለመተማመኑ ዑደት በቀላሉ እንደማይሰበር እንዳስብ አደረገኝ፡፡ እንዲያውም ግድያው ካቆመም በኋላ በእርግጠኝነት የባሰ መራር ሁኔታ ሊኖር ይችላል፤ ወደ ባሰ ሽብር የሚፈነዳ መራርነት፡፡ የእግዚአብሔር መለኮታዊ ምኅረት ብቻ ያንን አሁን ከመከሰት ያቆመው ይሆናል፡፡ በምንም ዓይነት መንገድ አምላክ ቢያስቀምጠኝ ያንን ማየት እችላለሁ - ሌሎች እንዲኖሩ ማድረግም የሕይወቴ ሥራ ዋነኛ ክፍል ይሆናል፡፡
በቀጣዩ ቀን መኰንኑ ቃሉን መጠበቁን አሳየ - ሁቱዎችን በእውነት ይጠላ ኖሯል፡፡ አንድ እየደማ ያለና ‹‹የዘር ጭፍጨፋ ተራፊ ነኝ፤ የቆሰልኩትም ከቱትሲ አማጽያን ጎን ስዋጋ ነው›› የሚል ሰው ወደ ምሽጉ ገብቶ ይዘዋወራል፡፡ መኰንኑ ግን ስላላመነው ወታደሮቹ አንበርክከውና ጠመንጃዎቻቸውን ራሱ ላይ ደግነው እንዲጠይቁት አደረገ፡፡ መጀመሪያ ላይ ሲጠይቁት የኢንተርሃምዌ አባል መሆኑን ካደ፡፡ ከብዙ ምርመራ በኋላ ግን ተስፋ ቆረጠና ተናዘዘ፡፡ መኰንኑም ለወታደሮቹ ራሱን ሲነቀንቅላቸው ጎትተው ወሰዱት፤ ከዚያ በኋላም በጭራሽ አላየነውም፡፡ ከወታደሮቹ አንደኛው በሌላ ጊዜ ሰውዬው የኢንተርሃምዌ ሰላይ እንደሆነ ማመኑን ነገረኝ፡፡
‹‹ስለሱ አትጨነቂ - ከአሁን በኋላ አያስቸግርሽም›› አለኝ፡፡
ለአክስቶቼና ለልጆቻቸው
በቻልኩት መጠን በቂ ምግብ መቅረቡን በማረጋገጥ፣ መድኃኒት ከወታደሮቹ በማምጣትና ቁስላቸውን በማከም እንክብካቤ አደረኩላቸው፡፡ እንዲያውም ምሽት ላይ እንዳይፈሩ በማሰብ በአቅራቢያቸው እተኛለሁ፡፡ ሆኖም ግን የሚጠበቅብኝን ያህል ጊዜ ከእነርሱ ጋር አላሳለፍኩም፡፡ በሕይወት በመቆየታቸውና ደኅና በመሆናቸው ደስተኛ ነኝ፡፡ ያም ሆኖ ግን ላጣሁት ቤተሰብ ምትክ አይሆኑኝም፡፡ አዲስ ሕይወት መጀመር እንዳለብኝ ተሰማኝ፡፡ በመታጠቢያ ቤቱ አብሬያቸው ከነበርኩት ሴቶች ጋር እንኳን መግባባቱ ከበደኝ፡፡ የምንኖረው በምሽጉ የተለየዩ ክፍሎች ተለያይተን ነው፡፡ እናም አንዳችን ላንዳችን ፈገግታ ብናሳይም ብዙም አንነጋገርም፡፡ በዚያች ጠባብ ስፍራ አብረን ለረጅም ጊዜ ብንቆይም እርስ በርሳችን በደንብ አልተዋወቅንም፡፡ የዘወትር ተግባቦታችን በእጅ ምልክቶችና በከንፈር ንባብ ስለነበር ፍራቻን፣ ሽብርንና ተስፋ መቁረጥን ያስተጋባል፡፡ ምናልባት በመታጠቢያ ቤቱ ልናወራ ችለን ቢሆን ኖሮ ጥሩ ወዳጆች ልንሆን እንችል ነበር፡፡ ሆኖም ግን ምሽጉ ውስጥ እርስ በርስ መተያየታችን ብዙ አሰቃቂ ትውስታዎቻችንን ይቀሰቅስብን ጀመር፡፡
ለማናቸውም አዳዲስ ሰው ለመተዋወቅ በርካታ ዕድሎች አሉን፡፡ ከጭፍጨፋው የተረፉ አዳዲስ የቱትሲ ስደተኞች በየቀኑ ይደርሱ ጀመር፡፡ ብዙዎቹ የተወዛገቡ፣ የተምታታባቸውና ኪንያሩዋንዳ ብቻ የሚናገሩ ናቸው፡፡ እኔ ሁለት ቋንቋ ስለምናገር መኰንኑ ሁሉንም አዲስ-ደራሽ ስደተኞች እንድመዘግብለት ጠየቀኝ፡፡ እኔም ለማገዝ ደስተኛ ነኝ፡፡ ዕድሜያቸውንና ስማቸውን እየመዘገብኩ ጉዳታቸውንና የሚያስፈልጋቸውን የሕክምና እርዳታ ለፈረንሳዮቹ ወታደሮች አሳውቃለሁ፡፡ የግል ታሪካቸውንና ያለፉበትን ችግር ሁሉ እጽፋለሁ፡፡ በዚህ ሂደትም ብዙ አሰቃቂ ታሪኮችን ሰምቻለሁ፡፡ ቢሆንም የተወሰኑ ዘላቂ ጓደኞችን አፍርቻለሁ፡፡ አንድ አዲስ ጓደኛ የሆነችኝ ፍሎረንስ ስትሆን በኔ ዕድሜ ያለች ማራኪና ሽቁጥቁጥ ስትል ፈገግታዋ የሚስብ ሴት ነበረች፡፡ በገጀራ ዓይኖቿ መካከል መትተዋት በፊቷ ላይ ቁልቁል ከሚታየው ጉልህ ጠባሳ በቀር የግምጃ እራፊ ትመስላለች፡፡ እንደ ሌሎቻችን ሁሉ አሰቃቂ የሆነውን ታሪኳን መዝግቤያለሁ፡፡ ፍሎረንስ የመጣችው ከኔ መንደር ብዙም ከማትርቅ ትንሽ ከተማ ነው፡፡ ጭፍጨፋው ሲጀምር ቤተሰቧና ሦስት መቶ ጎረቤቶቿ ገዳዮቹ የቤተክርስቲያንን ቅድስና ያከብራሉ ብለው በማሰብ በአቅራቢያቸው ባለች ቤተክርስቲያን ከለላ ይጠይቃሉ፡፡ ሆኖም ግን ቱትሲዎችን በአንድ ቤት ታጅበው ማግኘታቸው ለገዳዮቹ ነገሩን አቀለላቸው፡፡ በቤተክርስትያኒቱ ውስጥ ባሉ አግዳሚ ወንበሮች መካከል እየተራመዱ ገጀራዎቻቸውን በመደዳ ግራና ቀኝ እየሰነዘሩ ሰዉን ተራ በተራ መመድመድ አልከበዳቸውም፡፡
‹‹መሣሪያም ሆነ ራሳችንን የምንከላከልበት ምንም መንገድ አልነበረንም›› አለች ፍሎረንስ፡፡ ‹‹የተወሰነ ልመናና ጩኸት ቢሰማም ብዙዎቻችን እዚያ ተቀምጠን የምንታረድበትን ተራ እንጠባበቅ ጀመር፡፡ መገደል እንደሚገባን እንዳሰብን ነው የሆነው - በእርግጥ አግባብ እንደሆነ ሁሉ … ወደኔ ሲመጡ የማስታውሰው ብቸኛ ነገር ገጀራ ወደ ፊቴ ሲሰነዘር ነው፡፡ ከዚያም ወደ አስከሬን መጣያቸው ልጣል ተጭኜ በመወሰድ ላይ ሳለሁ ነቃሁ፡፡››
የፍሎሬንስ ጠባሳ ጥልቅ ቢሆንም ለሞት የሚያደርሳት ግን አልነበረም - ሆኖም ገዳዮቹ በአንድ የጭነት ተሽከርካሪ ላይ ከሌሎች አስከሬኖች ጋር ይወረውሯታል፡፡ ስትነቃ በወላጆቿ አስከሬን ላይ እንደሆነች ይገባታል፤ እህቷም ከነሱ በላይ ታቃስታለች፡፡
‹‹በእህቴ ደረት ላይ የተሰካ ጦር አየሁ … ልትሞት ትንሽ ቢቀራትም ግን በማጓራት ላይ ነበረች፡፡ ወደ እርሷ ለመቅረብ ስሞክር ከኛ ጋር ተሳፍረው ከነበሩት ገዳዮች አንዱ ስንቀሳቀስ አይቶ በቀስቱ ይጓጉጠኝ ጀመር፡፡ እዚህ፣ እዚህ፣ እዚህ ጋ ወጋኝ›› አለች ወደ ደረቷ፣ ሆዷና ጭኖቿ እያመለከተች፡፡ ‹‹ሲወጋኝ ምንም አልተንቀሳቀስኩም፤ እንዲያውም እግዚአብሔር ሕመሜን አርቆ ሕይወቴን እንዲያተርፋት ነበር የጠየቅሁት፡፡ ብዙ ስለደማሁ ገዳዩ የሞትኩ ሳይመስለው አይቀርም፡፡ የጭነት ተሸከርካሪው ከአካንያሩ ወንዝ በላይ ባለ ኢንተርሃምዌዎች ብዙውን ጊዜ አስከሬን የሚጥሉበት ገደል አፋፍ ላይ ቆመ፡፡
‹‹ሁሉንም አስከሬኖች በገደሉ ቁልቁል ሲወረውሯቸው ወንዙ ውስጥ ያርፋሉ›› ስትል ፍሎረንስ ቀጠለች፡፡ ‹‹እግሮቼን ይዘው አየር ላይ ሲወረውሩኝ አስታውሳለሁ፤ የወራጅ ውሃውም ድምፅ በርቀት ይሰማኛል፤ ግን መውደቄን አላስታውስም፡፡ በቀጣዩ ቀን ጠዋት ወንዙ ዳር ጭቃው ላይ ነቃሁ፡፡ ወላጆቼ፣ እህቴ፣ ሁሉ….. ም እዚያ ወድቀዋል፤ ነገር ግን ሁሉም ሞተዋል፡፡ ገደሉን ሽቅብ ሳየው እንዴት እንደዳንኩ ሊገባኝ አልቻለም - የተጣልንበት ጥልቀት ቢያንስ መቶ ሃያ ክንድ ይሆናል፡፡ ማመን የምችለው እግዚአብሔር ለአንድ ዓላማ እንዳተረፈኝ ብቻ ነው፡፡›› ፍሎረንስ በወንዙ ዳር ለአንድ ቀን ከተኛች በኋላ ተነሥታ መሄድ ቻለች፡፡ በአቅራቢያው ወዳለ የደግ ሁቱዎች ቤት የግዷን ሄደች፡፡ አስገብተውና ቁስሏን ጠራርገው ደበቋት፡፡ ‹‹ሕይወቴን ቢያድኑኝም ታዲያ›› ስትል ቀጠለች፤ ‹‹ልጃቸው በጠዋት ይወጣና የሚገደል ቱትሲ እስኪያጡ ድረስ ከኢንተርሃምዌዎች ጋር ሆኖ በከተማዬ ያሉ ቱትሲዎችን መግደሉን ቀጥሏል፡፡ ከዚያ በኋላ ለኔ ምንም ስሜት የሚሰጠኝ ነገር ጠፋ፣ ኢማኪዩሌ፡፡ እህቴና ወላጆቼ ሲሞቱ ለምን የተረፍኩ ይመስልሻል?››
‹‹እግዚአብሔር ለአንድ ዓላማ ነው ያተረፈሽ›› ስል መለስኩላት፡፡ ‹‹ታሪክሽን እየጻፍኩት ነው፤ አንድ ቀንም አንድ ሰው ያነበውና የተከሰተውን ችግር ሁሉ ይረዳበታል፡፡ አንቺ እንደኔ ነሽ፡፡ የተረፍሽው የደረሰብንን ሁሉ እንድትናገሪ ነው፡፡›› በስደተኞቹና በፈረንሳውያኑ አስተናጋጆቻችን መካከል ብዙ የትርጉም ሥራ ስለሠራሁ የተወሰኑትን ወታደሮች ላውቅ ቻልኩ፡፡ ከመካከላቸው ፒየር የተባለው ወታደር በፍቅር ዓይን ያየኝ ጀመር፡፡ የውስጠኛውን የምሽጉን ክፍል ቀን ላይ እንዲጠብቅ ተመድቧል፡፡ ሌሊት ግን ኮከቦቹን እያየሁ ስቀመጥ ከኔ ጋር በማውራት ጊዜውን ያሳልፋል፡፡ ፒየር በዕድሜ ከኔ በተወሰኑ ዓመታት የሚያንስ ወጣት ነው፡፡ ትሁት፣ ለሰው አሳቢና ጥሩ አድማጭም ነው፡፡ በኔ ቤተሰብና በመንደሬ ላይ ተከስቶ የነበረውን ነገር ነገርኩት፤ እርሱም ስለ ቤተሰቡ፣ በፈረንሳይ ስላሳለፈው ሕይወትና ወደ ሩዋንዳ ከመምጣቱ በፊት ስለተለያቸው ሴት የፍቅር ጓደኞቹ ነገረኝ፡፡ የወንድ ጓደኛ እንዳለኝም ሲጠይቀኝ ስለ ዮሃንስና ስለተለያየንበት መላ ቅጡ የጠፋበት መንገድ ነገርኩት፡፡
ከፒየር ጋር ስሆን በአብሮነቱ በጣም ደስተኝነት ይሰማኛል፡፡ ከእርሱ ጋር ማውራት አእምሮዬን ካለሁበት ገሃዳዊ እውነታ ቢያንስ በጊዜያዊነት ያወጣዋል፡፡ ጊዜው ሲሄድ ፒየር ከኔ ጋር የሚሆንባቸውን ሰበብ አስባቦች መፈላልግ አበዛ - የሚበላ ያመጣልኛል፣ ወደ ምንጭ ውሃ ልቀዳ ስሄድ ጥበቃ ያደርግልኛል፤ የማነባቸውን መጻሕፍትም እየያዘልኝ ይመጣል ጓደኞቹ ስለዚህ ጉዳይ ቢቀልዱበትም በእኔ በኩል ምንም ግድ አልሰጠኝም፡፡ በዘር ጭፍጨፋው የማይሰቃይ ጓደኛ ማፍራቴ ለኔ እፎይታ ነው፡፡ ተስፋዎቼንና ህልሞቼን ለእርሱ መንገርም እንደገና ሰው እንደሆንኩ እንዲሰማኝ አደረገኝ
አንድ ቀን ፖል የተባለው የፒየር ጓደኛ ይህ ወጣት ወታደር በኔ ፍቅር እንደተነካ ሲነግረኝ አሳቀኝ፡፡ ልብሶቼን አልቀየርኩ፤ ለሦስት ወራት ያህል
ገላዬን እንኳን በአግባቡ አልታጠብኩ
ለማናቸውም አዳዲስ ሰው ለመተዋወቅ በርካታ ዕድሎች አሉን፡፡ ከጭፍጨፋው የተረፉ አዳዲስ የቱትሲ ስደተኞች በየቀኑ ይደርሱ ጀመር፡፡ ብዙዎቹ የተወዛገቡ፣ የተምታታባቸውና ኪንያሩዋንዳ ብቻ የሚናገሩ ናቸው፡፡ እኔ ሁለት ቋንቋ ስለምናገር መኰንኑ ሁሉንም አዲስ-ደራሽ ስደተኞች እንድመዘግብለት ጠየቀኝ፡፡ እኔም ለማገዝ ደስተኛ ነኝ፡፡ ዕድሜያቸውንና ስማቸውን እየመዘገብኩ ጉዳታቸውንና የሚያስፈልጋቸውን የሕክምና እርዳታ ለፈረንሳዮቹ ወታደሮች አሳውቃለሁ፡፡ የግል ታሪካቸውንና ያለፉበትን ችግር ሁሉ እጽፋለሁ፡፡ በዚህ ሂደትም ብዙ አሰቃቂ ታሪኮችን ሰምቻለሁ፡፡ ቢሆንም የተወሰኑ ዘላቂ ጓደኞችን አፍርቻለሁ፡፡ አንድ አዲስ ጓደኛ የሆነችኝ ፍሎረንስ ስትሆን በኔ ዕድሜ ያለች ማራኪና ሽቁጥቁጥ ስትል ፈገግታዋ የሚስብ ሴት ነበረች፡፡ በገጀራ ዓይኖቿ መካከል መትተዋት በፊቷ ላይ ቁልቁል ከሚታየው ጉልህ ጠባሳ በቀር የግምጃ እራፊ ትመስላለች፡፡ እንደ ሌሎቻችን ሁሉ አሰቃቂ የሆነውን ታሪኳን መዝግቤያለሁ፡፡ ፍሎረንስ የመጣችው ከኔ መንደር ብዙም ከማትርቅ ትንሽ ከተማ ነው፡፡ ጭፍጨፋው ሲጀምር ቤተሰቧና ሦስት መቶ ጎረቤቶቿ ገዳዮቹ የቤተክርስቲያንን ቅድስና ያከብራሉ ብለው በማሰብ በአቅራቢያቸው ባለች ቤተክርስቲያን ከለላ ይጠይቃሉ፡፡ ሆኖም ግን ቱትሲዎችን በአንድ ቤት ታጅበው ማግኘታቸው ለገዳዮቹ ነገሩን አቀለላቸው፡፡ በቤተክርስትያኒቱ ውስጥ ባሉ አግዳሚ ወንበሮች መካከል እየተራመዱ ገጀራዎቻቸውን በመደዳ ግራና ቀኝ እየሰነዘሩ ሰዉን ተራ በተራ መመድመድ አልከበዳቸውም፡፡
‹‹መሣሪያም ሆነ ራሳችንን የምንከላከልበት ምንም መንገድ አልነበረንም›› አለች ፍሎረንስ፡፡ ‹‹የተወሰነ ልመናና ጩኸት ቢሰማም ብዙዎቻችን እዚያ ተቀምጠን የምንታረድበትን ተራ እንጠባበቅ ጀመር፡፡ መገደል እንደሚገባን እንዳሰብን ነው የሆነው - በእርግጥ አግባብ እንደሆነ ሁሉ … ወደኔ ሲመጡ የማስታውሰው ብቸኛ ነገር ገጀራ ወደ ፊቴ ሲሰነዘር ነው፡፡ ከዚያም ወደ አስከሬን መጣያቸው ልጣል ተጭኜ በመወሰድ ላይ ሳለሁ ነቃሁ፡፡››
የፍሎሬንስ ጠባሳ ጥልቅ ቢሆንም ለሞት የሚያደርሳት ግን አልነበረም - ሆኖም ገዳዮቹ በአንድ የጭነት ተሽከርካሪ ላይ ከሌሎች አስከሬኖች ጋር ይወረውሯታል፡፡ ስትነቃ በወላጆቿ አስከሬን ላይ እንደሆነች ይገባታል፤ እህቷም ከነሱ በላይ ታቃስታለች፡፡
‹‹በእህቴ ደረት ላይ የተሰካ ጦር አየሁ … ልትሞት ትንሽ ቢቀራትም ግን በማጓራት ላይ ነበረች፡፡ ወደ እርሷ ለመቅረብ ስሞክር ከኛ ጋር ተሳፍረው ከነበሩት ገዳዮች አንዱ ስንቀሳቀስ አይቶ በቀስቱ ይጓጉጠኝ ጀመር፡፡ እዚህ፣ እዚህ፣ እዚህ ጋ ወጋኝ›› አለች ወደ ደረቷ፣ ሆዷና ጭኖቿ እያመለከተች፡፡ ‹‹ሲወጋኝ ምንም አልተንቀሳቀስኩም፤ እንዲያውም እግዚአብሔር ሕመሜን አርቆ ሕይወቴን እንዲያተርፋት ነበር የጠየቅሁት፡፡ ብዙ ስለደማሁ ገዳዩ የሞትኩ ሳይመስለው አይቀርም፡፡ የጭነት ተሸከርካሪው ከአካንያሩ ወንዝ በላይ ባለ ኢንተርሃምዌዎች ብዙውን ጊዜ አስከሬን የሚጥሉበት ገደል አፋፍ ላይ ቆመ፡፡
‹‹ሁሉንም አስከሬኖች በገደሉ ቁልቁል ሲወረውሯቸው ወንዙ ውስጥ ያርፋሉ›› ስትል ፍሎረንስ ቀጠለች፡፡ ‹‹እግሮቼን ይዘው አየር ላይ ሲወረውሩኝ አስታውሳለሁ፤ የወራጅ ውሃውም ድምፅ በርቀት ይሰማኛል፤ ግን መውደቄን አላስታውስም፡፡ በቀጣዩ ቀን ጠዋት ወንዙ ዳር ጭቃው ላይ ነቃሁ፡፡ ወላጆቼ፣ እህቴ፣ ሁሉ….. ም እዚያ ወድቀዋል፤ ነገር ግን ሁሉም ሞተዋል፡፡ ገደሉን ሽቅብ ሳየው እንዴት እንደዳንኩ ሊገባኝ አልቻለም - የተጣልንበት ጥልቀት ቢያንስ መቶ ሃያ ክንድ ይሆናል፡፡ ማመን የምችለው እግዚአብሔር ለአንድ ዓላማ እንዳተረፈኝ ብቻ ነው፡፡›› ፍሎረንስ በወንዙ ዳር ለአንድ ቀን ከተኛች በኋላ ተነሥታ መሄድ ቻለች፡፡ በአቅራቢያው ወዳለ የደግ ሁቱዎች ቤት የግዷን ሄደች፡፡ አስገብተውና ቁስሏን ጠራርገው ደበቋት፡፡ ‹‹ሕይወቴን ቢያድኑኝም ታዲያ›› ስትል ቀጠለች፤ ‹‹ልጃቸው በጠዋት ይወጣና የሚገደል ቱትሲ እስኪያጡ ድረስ ከኢንተርሃምዌዎች ጋር ሆኖ በከተማዬ ያሉ ቱትሲዎችን መግደሉን ቀጥሏል፡፡ ከዚያ በኋላ ለኔ ምንም ስሜት የሚሰጠኝ ነገር ጠፋ፣ ኢማኪዩሌ፡፡ እህቴና ወላጆቼ ሲሞቱ ለምን የተረፍኩ ይመስልሻል?››
‹‹እግዚአብሔር ለአንድ ዓላማ ነው ያተረፈሽ›› ስል መለስኩላት፡፡ ‹‹ታሪክሽን እየጻፍኩት ነው፤ አንድ ቀንም አንድ ሰው ያነበውና የተከሰተውን ችግር ሁሉ ይረዳበታል፡፡ አንቺ እንደኔ ነሽ፡፡ የተረፍሽው የደረሰብንን ሁሉ እንድትናገሪ ነው፡፡›› በስደተኞቹና በፈረንሳውያኑ አስተናጋጆቻችን መካከል ብዙ የትርጉም ሥራ ስለሠራሁ የተወሰኑትን ወታደሮች ላውቅ ቻልኩ፡፡ ከመካከላቸው ፒየር የተባለው ወታደር በፍቅር ዓይን ያየኝ ጀመር፡፡ የውስጠኛውን የምሽጉን ክፍል ቀን ላይ እንዲጠብቅ ተመድቧል፡፡ ሌሊት ግን ኮከቦቹን እያየሁ ስቀመጥ ከኔ ጋር በማውራት ጊዜውን ያሳልፋል፡፡ ፒየር በዕድሜ ከኔ በተወሰኑ ዓመታት የሚያንስ ወጣት ነው፡፡ ትሁት፣ ለሰው አሳቢና ጥሩ አድማጭም ነው፡፡ በኔ ቤተሰብና በመንደሬ ላይ ተከስቶ የነበረውን ነገር ነገርኩት፤ እርሱም ስለ ቤተሰቡ፣ በፈረንሳይ ስላሳለፈው ሕይወትና ወደ ሩዋንዳ ከመምጣቱ በፊት ስለተለያቸው ሴት የፍቅር ጓደኞቹ ነገረኝ፡፡ የወንድ ጓደኛ እንዳለኝም ሲጠይቀኝ ስለ ዮሃንስና ስለተለያየንበት መላ ቅጡ የጠፋበት መንገድ ነገርኩት፡፡
ከፒየር ጋር ስሆን በአብሮነቱ በጣም ደስተኝነት ይሰማኛል፡፡ ከእርሱ ጋር ማውራት አእምሮዬን ካለሁበት ገሃዳዊ እውነታ ቢያንስ በጊዜያዊነት ያወጣዋል፡፡ ጊዜው ሲሄድ ፒየር ከኔ ጋር የሚሆንባቸውን ሰበብ አስባቦች መፈላልግ አበዛ - የሚበላ ያመጣልኛል፣ ወደ ምንጭ ውሃ ልቀዳ ስሄድ ጥበቃ ያደርግልኛል፤ የማነባቸውን መጻሕፍትም እየያዘልኝ ይመጣል ጓደኞቹ ስለዚህ ጉዳይ ቢቀልዱበትም በእኔ በኩል ምንም ግድ አልሰጠኝም፡፡ በዘር ጭፍጨፋው የማይሰቃይ ጓደኛ ማፍራቴ ለኔ እፎይታ ነው፡፡ ተስፋዎቼንና ህልሞቼን ለእርሱ መንገርም እንደገና ሰው እንደሆንኩ እንዲሰማኝ አደረገኝ
አንድ ቀን ፖል የተባለው የፒየር ጓደኛ ይህ ወጣት ወታደር በኔ ፍቅር እንደተነካ ሲነግረኝ አሳቀኝ፡፡ ልብሶቼን አልቀየርኩ፤ ለሦስት ወራት ያህል
ገላዬን እንኳን በአግባቡ አልታጠብኩ
‹‹አዬ፣ ፒየር እኮ ሁሌ ስላንቺ ነው የሚያወራው›› ሲል አረጋገጠልኝ፡፡ ‹‹‹በዚህ ሁሉ ነገር ውስጥ ብታልፍም ልቧ ክፍት ነው፤ ሳቂታነትና ጨዋታ-አዋቂነትም አላት› ይላል፡፡››
‹‹አይ ምነው በል! እንዲህ ስትቀልዱብኝ ጨዋታ አዋቂ መባል ይነሰኝ?›› አልኩት፡፡ ወዲያውኑ ግን ፖል ቀልዱን እንዳልሆነ ገባኝ - ፒየር በፍቅሬ ተቃጥሎ ኖሯል፡፡
በዚህ የፍቅር ገጠመኝ ኩራት ቢሰማኝም ፍላጎት አልነበረኝም፡፡ ቤተሰቤን አጥቻለሁ፤ የጦርነቱን መጨረሻ ለማየት እበቃ እንደሆን እንኳን እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ዮሃንስ እንደዚያ ከጣለኝ በኋላ በፍቅር ተስፋ ቆርጫለሁ፡፡ ያም ሆኖ ፒየር የተሰበረ ልቤ ሌላ ሰው ድጋሚ መውደድ መቻሉን እንድገነዘብ ረዳኝ፡፡
በዚያ ምሽት እየተጣራ መጥቶ ለእግር ጉዞ ሽርሽር እንዳካሂደው ሲጠይቀኝ ፍቅሩን በኔ ላይ እንዳያባክን ልነግረው ወሰንኩ፡፡ እርሱ ግን ከልቡና በፍቅር ሲናገር ያልተዘጋጀሁበት ነገር በመሆኑ አስደነገጠኝ፡፡
‹‹ኢማኪዩሌ በእውነት ለመናገር ከጓደኛ በላይ ሆነሽብኛል›› ሲል ከልቡ ነገረኝ፡፡ ‹‹በጣም ልዩ ሰው ነሽ፡፡ ጭፍጨፋው፣ ሕመሙ፣ በዙሪያችን ያለው አመፅ ሁሉ ባለበት ሁኔታ ልትሰሚ የምትፈልጊው የመጨረሻው ነገር ይህ ነው፡፡ ግን እንዲያው ካንቺ ፍቅር የያዘኝ ይመስለኛል፡፡ አብሮነትሽን እፈልጋለሁ፡፡›› ያን ሁሉ ሰዓት ሽርሽር ስናደርግ ብዙ እንዲናገር ብጠብቀውም ይቺን ብቻ ተናግሮ ዝም በማለቱና ያን ያህል ግልጽ በመሆኑ አስገረመኝ፡፡
‹‹ፒየር›› ስል በዝግታ መለስኩለት፤ ‹‹ልቤ በሰቆቃ ተሞልቷል፤ አሁን በልቤ ውስጥ የቀረችው ስፍራ ለፈጣሪዬ ብቻ የምትሆን ነች፡፡ በፍቅር መውደቅን ላስበው አልችልም… ወደፊት ለሚገጥሙኝ ፈተናዎች መስጠት ያለብኝን አትኩሮት ማጣት የለብኝም፡፡ ራሴን መንከባከብ እኮ ይኖርብኛል …››
እጄን ያዝ አደረገኝና ‹‹የምናገረው እኮ ከልቤ ነው … እወድሻለሁ፤ አሁንም እንከባከብሻለሁ፡፡ ካንቺ ጋር መሆን እፈልጋለሁ፤ ላጣሽ አልፈልግም፡፡›› ያን ያህል አውጥቶ በመናገሩ ትንሽ ተገርሜያለሁ፡፡ በእግዚአብሔር ፍቃድ ሳይሆን በአጋጣሚ የተገናኘን ሆኖ ተሰምቶኛል፡፡ ጌታዬ ዮሃንስን ለኔ የፈቀደልኝ ሰው እንዳልሆነ እንዳሳወቀኝ ሁሉ አሁን ፒየርንም እንደማይሆነኝ እያሳወቀኝ ነው፡፡ ይህን ጥያቄ በአዎንታ መቀበል ያለብኝ አይመስለኝም - ዝግጁ ስሆን እግዚአብሔር ፍቅረኛ እንደሚያመጣልኝ ታውቆኛል፡፡ ሲያመጣልኝም ምንም ዓይነት ጥርጣሬም ሆነ ማመንታት አይኖርም፡፡
‹‹አይ ፒየር … አይሆንም፡፡ አሁን ልቤ ከቆሙት ይልቅ ከሞቱት ዘንድ ነው - ማልቀስ እንኳን ገና አልጀመርኩም፡፡ ‹እዬዬም ሲዳላ ነው፡፡› ጓደኝነትህ ለኔ ትልቅ ነገሬ ስለሆነ ላቆየው እፈልጋለሁ፡፡ ስለዚህ እባክህ እንዲሁ ጓደኛሞች እንሁን፡፡››
‹‹አውቃለሁ›› አለ በብስጭት፡፡ ‹‹እንግዲህ ልብሽን ማግኘት ካልቻልኩ እየወደድኩሽም መለያየታችን ግድ ነው፡፡ እንዲሁ እንደዋዛ ደኅና ሁኚ ልበልሻ፣ በይ ደኅና እደሪ ሆዴ፡፡›› ዘንበል ብሎ አፌ ላይ በመሳም አስደነገጠኝ፡፡ የእርሱ ከንፈሮች የኔን ባገኙባት አፍታ ልቤ እንደ ሰም ስትቀልጥ ዓይኖቼን ጨፍኜ የመሳሜ ሙቀት ሕመሜንና ብስጭቴን አስረሳኝ፡፡ ፒየርም ሌሎቹን ወታደሮች ለመቀላቀል ሾር ብሎ ሲሄድ ፈገግታዬ እየከሰመ ሄደ፡፡ የቀረኝ ብቸኛ ነገር እንዳረክ አርገኝ ብዬ ሁሉን ነገር ለእግዚአብሔር መተው ነው፡፡
ላይሆንልኝ ነገር ለወንድሜ ለኤይማብል በሕይወት እንዳለሁ ላሳውቀው ፈለግሁ፣ ግን ምንም ዓይነት የመልዕክት መላላኪያም ሆነ የስልክ አገልግሎት የለም፡፡ የስልክ ቁጥሩም ሆነ የምከፍለው ገንዘብ የለኝም፡፡ ኤይማብል 5000 ኪሎሜትር ርቆ ሴኔጋል እየተማረ ስለሆነ እዚያው እንዲቀር ተመኘሁ፡፡ ወደ ሩዋንዳ ከተመለሰ እንደተቀረው ቤተሰቤ ሁሉ ይሞታል፡፡ ስለዚህ መልሼ የማገኘው ጦርነቱ ሲያልቅ ይሆናል፡፡ ግን መቼ ይሆን ጦርነቱ የሚያልቀው? ፈረንሳውያኑ ምንም ወሬ አልነገሩንም፤ የምናዳምጠው ሬድዮም የለን፡፡ ያሉን ብቸኞቹ የወሬ ምንጮች በእጅጉ ወደ ተጨናነቀው ምሽጋችን የሚመጡ አዳዲስ ገቢዎች ናቸው፡፡ በሐምሌ መጨረሻ አካባቢ ቱትሲዎቹ የሩአግ አማጽያን በሰሜን ድል ማድረጋቸውን ሰማሁ፤ በምሥራቅና በደቡብ ግን ጦርነቱ ቀጥሏል፡፡ ፈረንሳውያኑ በበኩላቸው እኛ ያለንበትን ምዕራብ ሩዋንዳን፣ የኪቩ ሐይቅን ዳርቻና የዛየርን ድንበር ጨምሮ ተቆጣጥረዋል፡፡ ለእኛ ጥሩ ዜና ቢሆንም ሁኔታው አሁንም እጅግ አደገኛ ነው፡፡ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሁቱ ስደተኞች የኪቩ ሐይቅን ለመጠጋትና ወደ ዛየር ለማምለጥ በመሞከር ላይ ናቸው፡፡
በየቀኑ አዳዲስ የተረፉ ቱትሲዎች በራችን ላይ ይመጣሉ፡፡ ወደ ምሽጉ ከደረስኩ ጀምሮ በሦስት ሳምንታት ቁጥራችን ከተወሰኑ ደርዘኖች ወደ 150 ገደማ አድጓል - እኔም የስደተኞቹን ታሪክና የጤና ሁኔታ እጽፋለሁ፡፡ ብዙዎቹ ስደተኞች አንድም እጅና እግሮቻቸውን አጥተዋል አለያም በሌሎች ዓይነት አሰቃቂ ግርፋቶች ሳቢያ ቋሚ አካላዊ ጉዳቶች ደርሰውባቸው በጽኑ ቆስለዋል፡፡ ብዙውን ጊዜ ቁስሎቻቸው ክፉኛ የተመረዙ ስለሚሆኑ እንደማይድኑ አውቃለሁ፡፡ እጅና እግሮቻቸውን ያላጡትም ቢሆኑ አብዛኛውን ጊዜ የሚመጡት የሚወዱትን በማጣት፣ በሐዘንና በአዕምሯቸው በተቀረጸው ሽብር ምክንያት አብደውና ራሳቸውን ስተው ነው ፡፡ በምሽጉ ውስጥ ካስቸገሩኝ ነገሮች አንዱ የወላጅ አልባዎች ነገር ነው፡፡ ለአብነት ዕድሜያቸው ሦስትና አራት ዓመት የነበረውን ከኪጋሊ ወደኛ የመጡትን ወንድማማቾች ፈጽሞ አልረሳቸውም፡፡ ገዳዮቹ ሲደርሱ ወላጆቻቸው በቤታቸው ኮርኒስ ላይ ይደብቋቸዋል፡፡ ወላጆቻቸው ሲገደሉ ልጆቹ ግን ከተወሰኑ ቀናት በኋላ በደግ ሁቱ ጎረቤቶቻቸው ተገኙ፡፡ እነርሱም ወደ ደቡብ ጦርነቱን ለማምለጥ ሲመጡ ያመጧቸዋል፡፡ ሰዎቹ ልጆቹን ለመውሰድ አዳጋች ወደሆነው ወደ ዛየር ሊሄዱ መሆኑን በመግለጽ ለፈረንሳውያን ወታደሮች ይሰጧቸዋል፡፡ ወታደሮቹም በአንዳንድ ምክንያቶች ሰበብ የልጆቹንም ሆነ የጎረቤቶቻቸውን ስም አልጻፉም፡፡ በተጨማሪም ሁለቱም ልጆች በምሽጋችን ሲደርሱ ከባድ ትኩሳት ይዟቸዋል፡፡ በምሽጋችን ውስጥ በጣም በዕድሜ ትንሾቹ ልጆች ምንም ሃይ ባይ ወላጅም ይሁን ዘመድ ስለሌላቸው ለጊዜው እኔው በማደጎ ተቀብዬ እንከባከባቸው ገባሁ፡፡ በፈረንሳዩ መኰንን እገዛ በመማሪያ ክፍሉ ውስጥ አልጋ ዘረጋሁላቸው፤ ትኩሳታቸውን የሚቀንስ መድኃኒትም አገኘሁላቸው፡፡
ሲናገሩ መስማቱ ልቤን ነካው፡፡ የወላጆቻቸውን አስከሬኖች ቢያዩም የሞትን አይምሬነት ለመረዳት ግን ዕድሜያቸው አይፈቅድም፡፡ ትልቀኛው ልጅ ታናሽ ወንድሙን ይንከባከባል፤ አዲስ ለሚያገኟቸው ሰዎችም ትሁት እንዲሆን ያሳስበዋል፡፡ ሦስት አመቱ የሆነው ልጅ ታላቅ ወንድሙን ፍሬንች ፍራይስ የሚባሉትን ጣፋጭ ምግቦችና ለስላሳ መጠጥ እንዲያመጣለት ይጨቀጭቀዋል፤ ታላቅየውም ሁልጊዜ በግሩም ትዕግሥት ይመልስለታል፡፡
‹‹እቤታችን እንዳልሆንን አስታውስ እንጂ … እዚህ ፍሬንች ፍራይስና ለስላሳ ልናገኝ አንችልም፡፡ እማማና አባባ መጥተው እስኪያገኙን መጠበቅ አለብን - ከዚያ ይሰጡናል፡፡ ማስቸገር የለብንም፣ መባለግ አያስፈልግም፤ ያለዚያ የባሰ ችግር ይደርስብናል፡፡›› ታናሽ ወንድሙ ሲያለቅስበት ‹‹አታልቅስ … እማማና አባባ ቶሎ ይመጣሉ፤ ከዚያ ፍሬንች ፍራይስ እንዳሻህ ትበላለህ፡፡ እንጠብቃቸው፤ እማማና አባባ ሁሉንም ነገር
ያስተካክሉልናል፡፡››
እነዚህ ልጆች
‹‹አይ ምነው በል! እንዲህ ስትቀልዱብኝ ጨዋታ አዋቂ መባል ይነሰኝ?›› አልኩት፡፡ ወዲያውኑ ግን ፖል ቀልዱን እንዳልሆነ ገባኝ - ፒየር በፍቅሬ ተቃጥሎ ኖሯል፡፡
በዚህ የፍቅር ገጠመኝ ኩራት ቢሰማኝም ፍላጎት አልነበረኝም፡፡ ቤተሰቤን አጥቻለሁ፤ የጦርነቱን መጨረሻ ለማየት እበቃ እንደሆን እንኳን እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ዮሃንስ እንደዚያ ከጣለኝ በኋላ በፍቅር ተስፋ ቆርጫለሁ፡፡ ያም ሆኖ ፒየር የተሰበረ ልቤ ሌላ ሰው ድጋሚ መውደድ መቻሉን እንድገነዘብ ረዳኝ፡፡
በዚያ ምሽት እየተጣራ መጥቶ ለእግር ጉዞ ሽርሽር እንዳካሂደው ሲጠይቀኝ ፍቅሩን በኔ ላይ እንዳያባክን ልነግረው ወሰንኩ፡፡ እርሱ ግን ከልቡና በፍቅር ሲናገር ያልተዘጋጀሁበት ነገር በመሆኑ አስደነገጠኝ፡፡
‹‹ኢማኪዩሌ በእውነት ለመናገር ከጓደኛ በላይ ሆነሽብኛል›› ሲል ከልቡ ነገረኝ፡፡ ‹‹በጣም ልዩ ሰው ነሽ፡፡ ጭፍጨፋው፣ ሕመሙ፣ በዙሪያችን ያለው አመፅ ሁሉ ባለበት ሁኔታ ልትሰሚ የምትፈልጊው የመጨረሻው ነገር ይህ ነው፡፡ ግን እንዲያው ካንቺ ፍቅር የያዘኝ ይመስለኛል፡፡ አብሮነትሽን እፈልጋለሁ፡፡›› ያን ሁሉ ሰዓት ሽርሽር ስናደርግ ብዙ እንዲናገር ብጠብቀውም ይቺን ብቻ ተናግሮ ዝም በማለቱና ያን ያህል ግልጽ በመሆኑ አስገረመኝ፡፡
‹‹ፒየር›› ስል በዝግታ መለስኩለት፤ ‹‹ልቤ በሰቆቃ ተሞልቷል፤ አሁን በልቤ ውስጥ የቀረችው ስፍራ ለፈጣሪዬ ብቻ የምትሆን ነች፡፡ በፍቅር መውደቅን ላስበው አልችልም… ወደፊት ለሚገጥሙኝ ፈተናዎች መስጠት ያለብኝን አትኩሮት ማጣት የለብኝም፡፡ ራሴን መንከባከብ እኮ ይኖርብኛል …››
እጄን ያዝ አደረገኝና ‹‹የምናገረው እኮ ከልቤ ነው … እወድሻለሁ፤ አሁንም እንከባከብሻለሁ፡፡ ካንቺ ጋር መሆን እፈልጋለሁ፤ ላጣሽ አልፈልግም፡፡›› ያን ያህል አውጥቶ በመናገሩ ትንሽ ተገርሜያለሁ፡፡ በእግዚአብሔር ፍቃድ ሳይሆን በአጋጣሚ የተገናኘን ሆኖ ተሰምቶኛል፡፡ ጌታዬ ዮሃንስን ለኔ የፈቀደልኝ ሰው እንዳልሆነ እንዳሳወቀኝ ሁሉ አሁን ፒየርንም እንደማይሆነኝ እያሳወቀኝ ነው፡፡ ይህን ጥያቄ በአዎንታ መቀበል ያለብኝ አይመስለኝም - ዝግጁ ስሆን እግዚአብሔር ፍቅረኛ እንደሚያመጣልኝ ታውቆኛል፡፡ ሲያመጣልኝም ምንም ዓይነት ጥርጣሬም ሆነ ማመንታት አይኖርም፡፡
‹‹አይ ፒየር … አይሆንም፡፡ አሁን ልቤ ከቆሙት ይልቅ ከሞቱት ዘንድ ነው - ማልቀስ እንኳን ገና አልጀመርኩም፡፡ ‹እዬዬም ሲዳላ ነው፡፡› ጓደኝነትህ ለኔ ትልቅ ነገሬ ስለሆነ ላቆየው እፈልጋለሁ፡፡ ስለዚህ እባክህ እንዲሁ ጓደኛሞች እንሁን፡፡››
‹‹አውቃለሁ›› አለ በብስጭት፡፡ ‹‹እንግዲህ ልብሽን ማግኘት ካልቻልኩ እየወደድኩሽም መለያየታችን ግድ ነው፡፡ እንዲሁ እንደዋዛ ደኅና ሁኚ ልበልሻ፣ በይ ደኅና እደሪ ሆዴ፡፡›› ዘንበል ብሎ አፌ ላይ በመሳም አስደነገጠኝ፡፡ የእርሱ ከንፈሮች የኔን ባገኙባት አፍታ ልቤ እንደ ሰም ስትቀልጥ ዓይኖቼን ጨፍኜ የመሳሜ ሙቀት ሕመሜንና ብስጭቴን አስረሳኝ፡፡ ፒየርም ሌሎቹን ወታደሮች ለመቀላቀል ሾር ብሎ ሲሄድ ፈገግታዬ እየከሰመ ሄደ፡፡ የቀረኝ ብቸኛ ነገር እንዳረክ አርገኝ ብዬ ሁሉን ነገር ለእግዚአብሔር መተው ነው፡፡
ላይሆንልኝ ነገር ለወንድሜ ለኤይማብል በሕይወት እንዳለሁ ላሳውቀው ፈለግሁ፣ ግን ምንም ዓይነት የመልዕክት መላላኪያም ሆነ የስልክ አገልግሎት የለም፡፡ የስልክ ቁጥሩም ሆነ የምከፍለው ገንዘብ የለኝም፡፡ ኤይማብል 5000 ኪሎሜትር ርቆ ሴኔጋል እየተማረ ስለሆነ እዚያው እንዲቀር ተመኘሁ፡፡ ወደ ሩዋንዳ ከተመለሰ እንደተቀረው ቤተሰቤ ሁሉ ይሞታል፡፡ ስለዚህ መልሼ የማገኘው ጦርነቱ ሲያልቅ ይሆናል፡፡ ግን መቼ ይሆን ጦርነቱ የሚያልቀው? ፈረንሳውያኑ ምንም ወሬ አልነገሩንም፤ የምናዳምጠው ሬድዮም የለን፡፡ ያሉን ብቸኞቹ የወሬ ምንጮች በእጅጉ ወደ ተጨናነቀው ምሽጋችን የሚመጡ አዳዲስ ገቢዎች ናቸው፡፡ በሐምሌ መጨረሻ አካባቢ ቱትሲዎቹ የሩአግ አማጽያን በሰሜን ድል ማድረጋቸውን ሰማሁ፤ በምሥራቅና በደቡብ ግን ጦርነቱ ቀጥሏል፡፡ ፈረንሳውያኑ በበኩላቸው እኛ ያለንበትን ምዕራብ ሩዋንዳን፣ የኪቩ ሐይቅን ዳርቻና የዛየርን ድንበር ጨምሮ ተቆጣጥረዋል፡፡ ለእኛ ጥሩ ዜና ቢሆንም ሁኔታው አሁንም እጅግ አደገኛ ነው፡፡ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሁቱ ስደተኞች የኪቩ ሐይቅን ለመጠጋትና ወደ ዛየር ለማምለጥ በመሞከር ላይ ናቸው፡፡
በየቀኑ አዳዲስ የተረፉ ቱትሲዎች በራችን ላይ ይመጣሉ፡፡ ወደ ምሽጉ ከደረስኩ ጀምሮ በሦስት ሳምንታት ቁጥራችን ከተወሰኑ ደርዘኖች ወደ 150 ገደማ አድጓል - እኔም የስደተኞቹን ታሪክና የጤና ሁኔታ እጽፋለሁ፡፡ ብዙዎቹ ስደተኞች አንድም እጅና እግሮቻቸውን አጥተዋል አለያም በሌሎች ዓይነት አሰቃቂ ግርፋቶች ሳቢያ ቋሚ አካላዊ ጉዳቶች ደርሰውባቸው በጽኑ ቆስለዋል፡፡ ብዙውን ጊዜ ቁስሎቻቸው ክፉኛ የተመረዙ ስለሚሆኑ እንደማይድኑ አውቃለሁ፡፡ እጅና እግሮቻቸውን ያላጡትም ቢሆኑ አብዛኛውን ጊዜ የሚመጡት የሚወዱትን በማጣት፣ በሐዘንና በአዕምሯቸው በተቀረጸው ሽብር ምክንያት አብደውና ራሳቸውን ስተው ነው ፡፡ በምሽጉ ውስጥ ካስቸገሩኝ ነገሮች አንዱ የወላጅ አልባዎች ነገር ነው፡፡ ለአብነት ዕድሜያቸው ሦስትና አራት ዓመት የነበረውን ከኪጋሊ ወደኛ የመጡትን ወንድማማቾች ፈጽሞ አልረሳቸውም፡፡ ገዳዮቹ ሲደርሱ ወላጆቻቸው በቤታቸው ኮርኒስ ላይ ይደብቋቸዋል፡፡ ወላጆቻቸው ሲገደሉ ልጆቹ ግን ከተወሰኑ ቀናት በኋላ በደግ ሁቱ ጎረቤቶቻቸው ተገኙ፡፡ እነርሱም ወደ ደቡብ ጦርነቱን ለማምለጥ ሲመጡ ያመጧቸዋል፡፡ ሰዎቹ ልጆቹን ለመውሰድ አዳጋች ወደሆነው ወደ ዛየር ሊሄዱ መሆኑን በመግለጽ ለፈረንሳውያን ወታደሮች ይሰጧቸዋል፡፡ ወታደሮቹም በአንዳንድ ምክንያቶች ሰበብ የልጆቹንም ሆነ የጎረቤቶቻቸውን ስም አልጻፉም፡፡ በተጨማሪም ሁለቱም ልጆች በምሽጋችን ሲደርሱ ከባድ ትኩሳት ይዟቸዋል፡፡ በምሽጋችን ውስጥ በጣም በዕድሜ ትንሾቹ ልጆች ምንም ሃይ ባይ ወላጅም ይሁን ዘመድ ስለሌላቸው ለጊዜው እኔው በማደጎ ተቀብዬ እንከባከባቸው ገባሁ፡፡ በፈረንሳዩ መኰንን እገዛ በመማሪያ ክፍሉ ውስጥ አልጋ ዘረጋሁላቸው፤ ትኩሳታቸውን የሚቀንስ መድኃኒትም አገኘሁላቸው፡፡
ሲናገሩ መስማቱ ልቤን ነካው፡፡ የወላጆቻቸውን አስከሬኖች ቢያዩም የሞትን አይምሬነት ለመረዳት ግን ዕድሜያቸው አይፈቅድም፡፡ ትልቀኛው ልጅ ታናሽ ወንድሙን ይንከባከባል፤ አዲስ ለሚያገኟቸው ሰዎችም ትሁት እንዲሆን ያሳስበዋል፡፡ ሦስት አመቱ የሆነው ልጅ ታላቅ ወንድሙን ፍሬንች ፍራይስ የሚባሉትን ጣፋጭ ምግቦችና ለስላሳ መጠጥ እንዲያመጣለት ይጨቀጭቀዋል፤ ታላቅየውም ሁልጊዜ በግሩም ትዕግሥት ይመልስለታል፡፡
‹‹እቤታችን እንዳልሆንን አስታውስ እንጂ … እዚህ ፍሬንች ፍራይስና ለስላሳ ልናገኝ አንችልም፡፡ እማማና አባባ መጥተው እስኪያገኙን መጠበቅ አለብን - ከዚያ ይሰጡናል፡፡ ማስቸገር የለብንም፣ መባለግ አያስፈልግም፤ ያለዚያ የባሰ ችግር ይደርስብናል፡፡›› ታናሽ ወንድሙ ሲያለቅስበት ‹‹አታልቅስ … እማማና አባባ ቶሎ ይመጣሉ፤ ከዚያ ፍሬንች ፍራይስ እንዳሻህ ትበላለህ፡፡ እንጠብቃቸው፤ እማማና አባባ ሁሉንም ነገር
ያስተካክሉልናል፡፡››
እነዚህ ልጆች
በምንም ተዓምር ወላጆቻቸውን በድጋሚ እንደማያዩ አውቃለሁ፤ ከሁኔታው መረዳት እንደሚቻለው ሁሉም ዘመዶቻቸው የሞቱ ሳይሆን አይቀርም፡፡ የወደፊት ሕይወታቸው በሐዘን፣ በመገፋትና የሚያስፈልጋቸውን በመነፈግ እንዳይሞላ ሠጋሁ - ምሬትና ጥላቻ በቀላሉ ስር የሚሰዱበት ዓይነት ሕይወት፡፡ በነዚያ ምስኪን ዓይኖች የጥላቻና ያለመተማመን ቀለበት ሲያደራ ይታየኛል፡፡ ስለሆነም እግዚአብሔር ለምን እንዳዳነኝ የሚያመለክት ሌላ ምክንያት እያሳየኝ እንደሆነ አውቄያለሁ፡፡ አንድ ቀን ስበረታና ዐቅም ሳገኝ በዘር ፍጅቱ ወላጆቻቸውን ያጡትን ልጆች ለማገዝ የምችለውን ሁሉ እንደማደርግ ቃል ገባሁ፡፡ በሕይወታቸው ላይ ተስፋና ደስታን ለማምጣትና ቤተሰቦቻቸውንና የቤተሰብ ፍቅርን የነጠቃቸውን ጥላቻን እንዲርቁ ለማድረግ እሞክራለሁ፡፡
በነሐሴ መጀመሪያ ላይ መኰንኑ ምሽጉ በጣም ስለሞላ አብዛኞቹን ስደተኞች ሊያጓጉዛቸው እንደሆነ ነገረኝ፡፡ አዲሱ ምሽግ በኪቡዬ ከተማ ባለ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ይሆናል፡፡ ንጹሕ ውሃ፣ የተሻለ ምግብና አልጋዎችም ይኖሩታል፡፡ እንዲመቻቸው ብዬ ‹‹ወንዶቹ ልጆቼ›› መጀመሪያ እንዲዛወሩ አደረግሁ፡፡ አክስቶቼና ልጆቻቸውም መሄዳቸውን አረጋገጥኩ - አዎን አሁን ተሽሏቸዋል፤ ግን የተሻለ ሰላም እንዲሰማቸው ከራሳቸው በላይ ጣራና በዙሪያቸው ግድግዳ ያስፈልጋቸዋል፡፡ ሄጄ ሁሉንም ሰው ለመንከባከብ ባቅድም መኰንኑ ቀርቼ በምሽጉ ባለው ሥራ እንዳግዝ ለመነኝ፡፡ አሁንም ቢሆን አስተርጓሚ ያስፈልጋቸዋል፡፡ በተጨማሪም አዳዲስ በሕይወት የተረፉ ሰዎችም መግባታቸውን ቀጥለዋል፡፡
‹‹ያው ከቆየሽ ሕይወት ታድኛለሽ›› ሲል ነገረኝ፡፡ እንዴት አሻፈረኝ እለዋለሁ? እዚያው ቀረሁ፤ ትንንሾቹን ወንድማማቾችም ከዚያን ጊዜ በኋላ ፈጽሞ አላየኋቸውም፡፡ ሌሎች በረብሻ ወላጆቻቸውን ያጡ ልጆችን ለመንከባከብ የገባሁትን ቃል ግን አልረሳሁትም፡፡ በሩዋንዳ የእነዚህ ዓይነት ልጆች እጥረትም የለም፡፡ በአሮጌው ምሽግ 30 የሚሆኑ ስደተኞች ሲቀሩ ከነርሱ ውስጥ ስምንቱ ፍሎሬንስና ዢን ፖልን ዓይነቶቹ አዲስ ያፈራኋቸው ጓደኞቼ ናቸው፡፡ በጣም ቅርብ የሆኑ አባላትን የያዘችው ትንሿ ቡድናችን እንደ አነስተኛ ቤተሰብ ሆነች፡፡ በእርግጥ ትሥሥራችን በጣም የጠበቀ ስለሆነ ዘጠኛችንም በአንድ ላይ ሆነን ካልሆነ በስተቀር ከምሽጉ አንዛወርም አልን፡፡
ቱትሲ ተፈናቃዮችን መቀበላችንን ብንቀጥልም መጠለያው ግን እያገለገለ ያለው እንደ መሸጋገሪያ ጣቢያ ነው፡፡ በሕይወት የተረፉትን እመዘግብና በአንድ ወይንም በሁለት ቀናት ውስጥ በከተማው ወዳለ ትልቅ መጠለያ እንዲዛወሩ እናደርጋለን፡፡ ከዚያም በነሐሴ መጀመሪያ ለወራት ያልሰማሁትን ነገር ሰማሁ - ጥልቅ፣ የሚያሽካካና ከልብ የሆነ ሣቅ፡፡ ከአዲሶቹ መጭዎች ስደተኞች ጋር ከመጣች አንዲት ሴትዮ ነው ሳቁ የመጣው፡፡ በተሸከርካሪ ወንበር ላይ ተቀምጣ በሰው እየተገፋች የምትሄደውን ይህች ሴትዮ ወታደሮቹ ከመጣችበት የጭነት ተሸከርካሪ እያወረዷት ነው፡፡ ወፍራም ስለሆነችና እግሮቿም በሽተኛ ስለሆኑ መራመድ እንደማትችል አውቄያለሁ፡፡ ይህ ሁሉ መከፋት ባለበት ምን የሚያስቅ ነገር አገኘች ብዬ ተገረምኩ፡፡ በኋላ ሲገባኝ የምትስቀው በሕይወት በመትረፏ ደስታ ተሰምቷት ኖሯል፡፡ወታደሮቹ በጥንቃቄ ተሸከርካሪ ወንበሯን መሬት ላይ ሲያስቀምጡላትና ሁለት ትንንሽ ልጆቿን ሲሰጧት አየሁ፡፡ ልጆቿ የፊቷን የተለያዩ ክፍሎች ሳሟት፤ እንደገናም ትስቅ ገባች - ሳቋም በመጠለያውም ግቢ አስተጋባ፡፡
‹‹አሎይዜ ነች›› አለ ዢን ፖል፡፡ ‹‹በመጠለያችን አንድ ታዋቂ ሰው ገባ ማለት ነው፡፡››
በእርግጥ ስለ አሎይዜ ሰምቼ ነበር፡፡ በልጅነቴ አንድ ሰው ጠንክሮ በመሥራትና በቁርጠኝነት በሕይወቱ የት እንደሚደርስ እርሷን በአርዓያነት እያነሱ ወላጆቼ በጣም ሲያወሩላት ሰምቻለሁ፡፡ አሎይዜ በዘጠኝ ዓመቷ የልጅነት ልምሻ ይዟት መራመድ ቢሳናትም በትምህርቷ ጥሩ ውጤት በማምጣት በሩዋንዳ ካሉ እጅግ ጎበዝ ልጆች አንዷ ለመሆን እንደበቃች ነግረውኛል፡፡ ስለሷ ከሰማሁት የማስታውሰው ያንን ብቻ ነው፤ ግን እንደተባለው በሀገሪቱ ዝና በማግኘቷ በመጠለያው ያሉ ብዙ ሰዎች ስለ እርሷ ሰምተዋል፡፡
ዢን ፖል እንደነገረኝ ባሏ ኪጋሊ ላይ በተመድ ውስጥ ይሠራ ስለነበር አሎይዜ ሁሉንም የሌሎች መንግሥታት መልዕክተኞች ማወቅ ችላለች፡፡ ‹‹ሁሉንም ሰው ስለምታውቅ ለማንም ቢሆን ጥሩ ሥራ ማግኘት ትችላለች›› አለኝ በአድናቆት፡፡ ሰዎች ‹‹አካል ጉዳተኛ ባትሆን ኖሮ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን ትችል ነበር ይላሉ፡፡ ቱትሲ እንደሆነች አውቃለሁ፤ ግን የመንግሥት ኮንትራቶችን ለማግኘት ስትል የሁቱ መታወቂያ ደብተር ከዓመታት በፊት ገዝታለች … ይገርምሻል በጣም ቆራጥ ሴት ነች፡፡››
‹‹እንግዲህ ሄጄ ይህችን ዝነኛ እንግዳችንን እመዘግባታለሁ›› ብዬ ደብተሬን ያዝኩና ወደ ተሸከርካሪው ሄድኩ፡፡
አሎይዜ ከተቀመጠችበት ወንበር ሽቅብ እያየችኝ ደስታዋ ወዲያውኑ ተኖ ታለቅስ ጀመር፡፡ ‹‹ወይኔ አምላኬ፣ እናትሽን ቁርጥ እኮ ነሽ … አባትሽንስ ቢሆን! ሁልጊዜ አንቺንም ሆነ ቤተሰብሽን እጠይቃችኋለሁ እያልኩ አስብ ነበር፤ ሆኖም አልቻልኩም፡፡ ምን ይሄን እግር ይዤ እንዴት ይሁንልኝ!
ሴትዮዋ ራሷን የሳተች ወይንም ሌላ ሰው መስያት የተምታታባት መሰለኝ፡፡ እስካሁን አግኝቻት አላውቅ፤ ታዲያ ማንነቴን እንዴት ልታውቅ ትችላለች?
‹‹አእምሮዬን እንደሳትኩ አድርገሽ አትዪኝ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ፡፡ ማን እንደሆንሽ በደንብ አውቃለሁ፡፡ አምላክ ነፍሳቸውን በገነት ያኑርልንና ወላጆችሽ - በጣም ጥሩ ወዳጆቼ ነበሩ፡፡›› አሎይዜ ልጆቿን አስቀምጣ፣ እንባዋን አባብሳ እጆቿን ዘረጋችልኝ፡፡ እንደዋዛ ቀረብ ብዬ እጆቼን ለሰላምታ ስዘረጋላት ክርኔን አፈፍ አድርጋ ጎትታ በደንብ አቀፈችኝ፡፡ ልትለቀኝ አልቻለችም፡፡ ‹‹እናትሽ ሕይወቴን አትርፋኛለች - ያን እንደማታውቂ እወራረዳለሁ! የስምንት ዓመት ልጅ ሳለሁ እናትሽ ትምህርት ብወድም ወላጆቼ ግን ሊያስተምሩኝ አቅሙ እንዳልነበራቸው ትሰማለች፡፡ እናም የአንድ ዓመት የትምህርት ክፍያዬን ሸፈነችልኝ … ታምሜ መራመድ ባቃተኝ ጊዜ እንኳን መክፈሏን ቀጠለች፡፡ በጣም ውለታዋ ስለከበደኝም በሕይወቴ አንድ ደረጃ ላይ መድረስ አለብኝ ብዬ ከማውቀው ከማንም ሰው አጠናን በላይ ማጥናት ጀመርኩ፡፡ ኢማኪዩሌ አሁን ያለኝ ነገር ሁሉ በእናትሽ ውለታ የተገኘ ነው፡፡ መልአክ ነበረች! አሎይዜ በስተመጨረሻም ከረጅም ጊዜ እቅፏ ስትለቀኝ ወደኋላዬ ተንገዳገድኩ፡፡ ከዚህች ጎበዝ ሴት ጋር በገጠመኝ በእንግዳው ክስተትም ተደናግጬ ራሴን ለማረጋጋት ራቅ ብሎ መሄድ አስፈለገኝ፡፡ ‹‹እስኪ ላንቺና ለልጆችሽ ትንሽ ምግብና ውሃ ልፈልግላችሁ›› አልኳት፡፡ ‹‹አሁኑኑ ተመልሼ እመጣና እመዘግባችኋለሁ፡፡››
እየሄድኩ ሳለሁ አሎይዜ ጠርታኝ ‹‹ኢማኪዩሌ እዚህ አንቺ ጋ ያመጣኝ የእናትሽ መንፈስ ነው መሰለኝ! ብድሯ ስላለብኝ አንቺን በማገዝ እከፍለዋለሁ፡፡ እስኪ ላስብበት፣ አንቺን የምረዳበትን መንገድ ልፈልግ›› አለችኝ፡፡
አንዲት በተሸከርካሪ ወንበር የምትሄድና እገዛዋን የሚፈልጉ ሁለት ትንንሽ ልጆች ያሏት ሴትዮ ምን ልታግዘኝ እንደምትችል እያሰብኩ ለሰላምታ እጄን አውለበለብኩና መንገዴን ቀጠልኩ፡፡ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እግዚአብሔር በተዓምራዊ መንገዶች እንደሚሄድ ሊያስተምረኝ ነው፡፡
በቀጣዩ ቀን አሎይዜን ስመዘግባት
በነሐሴ መጀመሪያ ላይ መኰንኑ ምሽጉ በጣም ስለሞላ አብዛኞቹን ስደተኞች ሊያጓጉዛቸው እንደሆነ ነገረኝ፡፡ አዲሱ ምሽግ በኪቡዬ ከተማ ባለ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ይሆናል፡፡ ንጹሕ ውሃ፣ የተሻለ ምግብና አልጋዎችም ይኖሩታል፡፡ እንዲመቻቸው ብዬ ‹‹ወንዶቹ ልጆቼ›› መጀመሪያ እንዲዛወሩ አደረግሁ፡፡ አክስቶቼና ልጆቻቸውም መሄዳቸውን አረጋገጥኩ - አዎን አሁን ተሽሏቸዋል፤ ግን የተሻለ ሰላም እንዲሰማቸው ከራሳቸው በላይ ጣራና በዙሪያቸው ግድግዳ ያስፈልጋቸዋል፡፡ ሄጄ ሁሉንም ሰው ለመንከባከብ ባቅድም መኰንኑ ቀርቼ በምሽጉ ባለው ሥራ እንዳግዝ ለመነኝ፡፡ አሁንም ቢሆን አስተርጓሚ ያስፈልጋቸዋል፡፡ በተጨማሪም አዳዲስ በሕይወት የተረፉ ሰዎችም መግባታቸውን ቀጥለዋል፡፡
‹‹ያው ከቆየሽ ሕይወት ታድኛለሽ›› ሲል ነገረኝ፡፡ እንዴት አሻፈረኝ እለዋለሁ? እዚያው ቀረሁ፤ ትንንሾቹን ወንድማማቾችም ከዚያን ጊዜ በኋላ ፈጽሞ አላየኋቸውም፡፡ ሌሎች በረብሻ ወላጆቻቸውን ያጡ ልጆችን ለመንከባከብ የገባሁትን ቃል ግን አልረሳሁትም፡፡ በሩዋንዳ የእነዚህ ዓይነት ልጆች እጥረትም የለም፡፡ በአሮጌው ምሽግ 30 የሚሆኑ ስደተኞች ሲቀሩ ከነርሱ ውስጥ ስምንቱ ፍሎሬንስና ዢን ፖልን ዓይነቶቹ አዲስ ያፈራኋቸው ጓደኞቼ ናቸው፡፡ በጣም ቅርብ የሆኑ አባላትን የያዘችው ትንሿ ቡድናችን እንደ አነስተኛ ቤተሰብ ሆነች፡፡ በእርግጥ ትሥሥራችን በጣም የጠበቀ ስለሆነ ዘጠኛችንም በአንድ ላይ ሆነን ካልሆነ በስተቀር ከምሽጉ አንዛወርም አልን፡፡
ቱትሲ ተፈናቃዮችን መቀበላችንን ብንቀጥልም መጠለያው ግን እያገለገለ ያለው እንደ መሸጋገሪያ ጣቢያ ነው፡፡ በሕይወት የተረፉትን እመዘግብና በአንድ ወይንም በሁለት ቀናት ውስጥ በከተማው ወዳለ ትልቅ መጠለያ እንዲዛወሩ እናደርጋለን፡፡ ከዚያም በነሐሴ መጀመሪያ ለወራት ያልሰማሁትን ነገር ሰማሁ - ጥልቅ፣ የሚያሽካካና ከልብ የሆነ ሣቅ፡፡ ከአዲሶቹ መጭዎች ስደተኞች ጋር ከመጣች አንዲት ሴትዮ ነው ሳቁ የመጣው፡፡ በተሸከርካሪ ወንበር ላይ ተቀምጣ በሰው እየተገፋች የምትሄደውን ይህች ሴትዮ ወታደሮቹ ከመጣችበት የጭነት ተሸከርካሪ እያወረዷት ነው፡፡ ወፍራም ስለሆነችና እግሮቿም በሽተኛ ስለሆኑ መራመድ እንደማትችል አውቄያለሁ፡፡ ይህ ሁሉ መከፋት ባለበት ምን የሚያስቅ ነገር አገኘች ብዬ ተገረምኩ፡፡ በኋላ ሲገባኝ የምትስቀው በሕይወት በመትረፏ ደስታ ተሰምቷት ኖሯል፡፡ወታደሮቹ በጥንቃቄ ተሸከርካሪ ወንበሯን መሬት ላይ ሲያስቀምጡላትና ሁለት ትንንሽ ልጆቿን ሲሰጧት አየሁ፡፡ ልጆቿ የፊቷን የተለያዩ ክፍሎች ሳሟት፤ እንደገናም ትስቅ ገባች - ሳቋም በመጠለያውም ግቢ አስተጋባ፡፡
‹‹አሎይዜ ነች›› አለ ዢን ፖል፡፡ ‹‹በመጠለያችን አንድ ታዋቂ ሰው ገባ ማለት ነው፡፡››
በእርግጥ ስለ አሎይዜ ሰምቼ ነበር፡፡ በልጅነቴ አንድ ሰው ጠንክሮ በመሥራትና በቁርጠኝነት በሕይወቱ የት እንደሚደርስ እርሷን በአርዓያነት እያነሱ ወላጆቼ በጣም ሲያወሩላት ሰምቻለሁ፡፡ አሎይዜ በዘጠኝ ዓመቷ የልጅነት ልምሻ ይዟት መራመድ ቢሳናትም በትምህርቷ ጥሩ ውጤት በማምጣት በሩዋንዳ ካሉ እጅግ ጎበዝ ልጆች አንዷ ለመሆን እንደበቃች ነግረውኛል፡፡ ስለሷ ከሰማሁት የማስታውሰው ያንን ብቻ ነው፤ ግን እንደተባለው በሀገሪቱ ዝና በማግኘቷ በመጠለያው ያሉ ብዙ ሰዎች ስለ እርሷ ሰምተዋል፡፡
ዢን ፖል እንደነገረኝ ባሏ ኪጋሊ ላይ በተመድ ውስጥ ይሠራ ስለነበር አሎይዜ ሁሉንም የሌሎች መንግሥታት መልዕክተኞች ማወቅ ችላለች፡፡ ‹‹ሁሉንም ሰው ስለምታውቅ ለማንም ቢሆን ጥሩ ሥራ ማግኘት ትችላለች›› አለኝ በአድናቆት፡፡ ሰዎች ‹‹አካል ጉዳተኛ ባትሆን ኖሮ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን ትችል ነበር ይላሉ፡፡ ቱትሲ እንደሆነች አውቃለሁ፤ ግን የመንግሥት ኮንትራቶችን ለማግኘት ስትል የሁቱ መታወቂያ ደብተር ከዓመታት በፊት ገዝታለች … ይገርምሻል በጣም ቆራጥ ሴት ነች፡፡››
‹‹እንግዲህ ሄጄ ይህችን ዝነኛ እንግዳችንን እመዘግባታለሁ›› ብዬ ደብተሬን ያዝኩና ወደ ተሸከርካሪው ሄድኩ፡፡
አሎይዜ ከተቀመጠችበት ወንበር ሽቅብ እያየችኝ ደስታዋ ወዲያውኑ ተኖ ታለቅስ ጀመር፡፡ ‹‹ወይኔ አምላኬ፣ እናትሽን ቁርጥ እኮ ነሽ … አባትሽንስ ቢሆን! ሁልጊዜ አንቺንም ሆነ ቤተሰብሽን እጠይቃችኋለሁ እያልኩ አስብ ነበር፤ ሆኖም አልቻልኩም፡፡ ምን ይሄን እግር ይዤ እንዴት ይሁንልኝ!
ሴትዮዋ ራሷን የሳተች ወይንም ሌላ ሰው መስያት የተምታታባት መሰለኝ፡፡ እስካሁን አግኝቻት አላውቅ፤ ታዲያ ማንነቴን እንዴት ልታውቅ ትችላለች?
‹‹አእምሮዬን እንደሳትኩ አድርገሽ አትዪኝ ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ፡፡ ማን እንደሆንሽ በደንብ አውቃለሁ፡፡ አምላክ ነፍሳቸውን በገነት ያኑርልንና ወላጆችሽ - በጣም ጥሩ ወዳጆቼ ነበሩ፡፡›› አሎይዜ ልጆቿን አስቀምጣ፣ እንባዋን አባብሳ እጆቿን ዘረጋችልኝ፡፡ እንደዋዛ ቀረብ ብዬ እጆቼን ለሰላምታ ስዘረጋላት ክርኔን አፈፍ አድርጋ ጎትታ በደንብ አቀፈችኝ፡፡ ልትለቀኝ አልቻለችም፡፡ ‹‹እናትሽ ሕይወቴን አትርፋኛለች - ያን እንደማታውቂ እወራረዳለሁ! የስምንት ዓመት ልጅ ሳለሁ እናትሽ ትምህርት ብወድም ወላጆቼ ግን ሊያስተምሩኝ አቅሙ እንዳልነበራቸው ትሰማለች፡፡ እናም የአንድ ዓመት የትምህርት ክፍያዬን ሸፈነችልኝ … ታምሜ መራመድ ባቃተኝ ጊዜ እንኳን መክፈሏን ቀጠለች፡፡ በጣም ውለታዋ ስለከበደኝም በሕይወቴ አንድ ደረጃ ላይ መድረስ አለብኝ ብዬ ከማውቀው ከማንም ሰው አጠናን በላይ ማጥናት ጀመርኩ፡፡ ኢማኪዩሌ አሁን ያለኝ ነገር ሁሉ በእናትሽ ውለታ የተገኘ ነው፡፡ መልአክ ነበረች! አሎይዜ በስተመጨረሻም ከረጅም ጊዜ እቅፏ ስትለቀኝ ወደኋላዬ ተንገዳገድኩ፡፡ ከዚህች ጎበዝ ሴት ጋር በገጠመኝ በእንግዳው ክስተትም ተደናግጬ ራሴን ለማረጋጋት ራቅ ብሎ መሄድ አስፈለገኝ፡፡ ‹‹እስኪ ላንቺና ለልጆችሽ ትንሽ ምግብና ውሃ ልፈልግላችሁ›› አልኳት፡፡ ‹‹አሁኑኑ ተመልሼ እመጣና እመዘግባችኋለሁ፡፡››
እየሄድኩ ሳለሁ አሎይዜ ጠርታኝ ‹‹ኢማኪዩሌ እዚህ አንቺ ጋ ያመጣኝ የእናትሽ መንፈስ ነው መሰለኝ! ብድሯ ስላለብኝ አንቺን በማገዝ እከፍለዋለሁ፡፡ እስኪ ላስብበት፣ አንቺን የምረዳበትን መንገድ ልፈልግ›› አለችኝ፡፡
አንዲት በተሸከርካሪ ወንበር የምትሄድና እገዛዋን የሚፈልጉ ሁለት ትንንሽ ልጆች ያሏት ሴትዮ ምን ልታግዘኝ እንደምትችል እያሰብኩ ለሰላምታ እጄን አውለበለብኩና መንገዴን ቀጠልኩ፡፡ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እግዚአብሔር በተዓምራዊ መንገዶች እንደሚሄድ ሊያስተምረኝ ነው፡፡
በቀጣዩ ቀን አሎይዜን ስመዘግባት
በሕግ ሁቱ ብትሆንም ባሏ ፋሪ፣ ቱትሲ እንደሆነ ነገረችኝ፡፡ ያም ማለት ልጀቿ ሳሚና ኬንዛ እንደ ቱትሲ ይቆጠራሉ ማለት ነው፡፡ ለልጆቿ ደህንነት በማሰብ በኪጋሊ ያለውን ቤታቸውን ትታ ወደ ወላጆቿ ቤት ለመደበቅ ሄደች፡፡ ባሏ እሷ ስትሄድ ኮርኒስ ውስጥ የተደበቀ ቢሆንም ይዳን ይሙት የምታውቀው ነገር የለም፡፡
‹‹የእናትሽን ውለታ ለመክፈል ምን ማድረግ እንዳለብኝ ወስኛለሁ›› አለች አሎይዜ፡፡ ‹‹ጦርነቱ ሙሉ በሙሉ እንዳበቃ ኪጋሊ ወዳለው ቤቴ እወስድሻለሁ፡፡ እንደራሳችን ልጅ ሆነሽ መኖር ትችያለሽ፡፡››
ስለ አሎይዜ ያላመንኩት አንድ ነገር አለ፡፡ ፈገግ ብዬ ስለ ቸርነቷ አመሰገንኳት፡፡ ቢሆንም በመጠለያው የተወሰኑ ጓደኛ ቤተሰቦች እንዳሉኝና አብረን ለመሆን ቃል እንደተገባባንም ነገርኳት፡፡ ትከሻዎቿን ነቅንቃ ከማምናቸው ሰዎች ጋር ለመቆየት መወሰኔ ግሩም ብልሃት መሆኑን ነገረችኝ፡፡ በዚያ ነገሩ ሁሉ የተቋጨ መስሎኛል፤ ሆኖም ግን በቀጣዩ ቀን ይህች ሴትዮ ከጓደኞቼ ጋር በተቀመጥኩበት መጣች፡፡
‹‹ኢማኪዩሌ ጉዳዩን አስቤበታለሁ፤ ታግተኛለች ብለሽ ካሰብሽ ጓደኞችሽን ሁሉ ወደ ኪጋሊ ማምጣት ትችያለሽ፡፡ ዘጠኛችሁንም በቤቴ አስቀምጣችኋለሁ! ቢጣበብም ይመቻል፡፡››
እርስ በርሳችን ተያይተን ተሣሣቅን፡፡ እንደዚህ ያለ እንግዳና ቸርነት የሚታይበትን ስጦታ እንዴት እንደምንቀበለው አናውቅበት አልን፡፡
‹‹አስቡበት›› አለች አሎይዜ ወንበሯን እያሽከረከረች በመሄድ ላይ ሳለች፡፡ ‹‹ከጦርነቱ በኋላ ለማድረግ የምታስቡት ሌላ ምን እንዳለ አላውቅም፡፡ ሁላችሁም ተሸብራችኋል … እናንተ ልጆች እዚያች ከተማ ባለ ምርጥ ቤት ኑሩ ብዬ ልለምናችሁ መገደዴን ላምን አልችልም፡፡ ጦርነቱ እያለቀ ነው - ስለ ወደፊቱ ሕይወታችሁ ማሰብ ጀምሩ እንጂ!››
አሎይዜ ትክክል ነች፡፡ ዋና ከተማዋ በአማጽያኑ ቁጥጥር ስር ውላለች፤ ጦርነቱም ፍጻሜ ሊያገኝ የጊዜ ጉዳይ ብቻ ነው፡፡ ሁላችንም ቤተሰቦቻችንን፣ ቤታችንንና ልብሳችንን ሳይቀር ያጣን ሲሆን ከኛ መካከል አንዲት እንኳን ሳንቲም ያለው ሰው የለም፡፡ የአሎይዜን ችሮታ መቀበል ጥሩ ውሳኔ መሆኑን ለመወሰን ረጅም ጊዜ አልወሰደብንም፡፡ በማግስቱም ችሮታዋን ለመቀበልና ለማመስገን በአንድነት ሄድን፡፡
‹‹እኔን አታመስግኑኝ፤ የኢማኪዩሌን እናት እንጂ›› አለች፡፡ ‹‹ይህን የማደርገው ስለ ሮዝ እንጂ ስለ እናንተ አይደለም!››
ለራሷ መሣቅ ጀመረች፤ ከዚያም እንደገና ልባዊ የደስታ ሣቅ በምሽጉ ሙሉ እስኪያስተጋባ ድረስ ቀጠለች፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
‹‹የእናትሽን ውለታ ለመክፈል ምን ማድረግ እንዳለብኝ ወስኛለሁ›› አለች አሎይዜ፡፡ ‹‹ጦርነቱ ሙሉ በሙሉ እንዳበቃ ኪጋሊ ወዳለው ቤቴ እወስድሻለሁ፡፡ እንደራሳችን ልጅ ሆነሽ መኖር ትችያለሽ፡፡››
ስለ አሎይዜ ያላመንኩት አንድ ነገር አለ፡፡ ፈገግ ብዬ ስለ ቸርነቷ አመሰገንኳት፡፡ ቢሆንም በመጠለያው የተወሰኑ ጓደኛ ቤተሰቦች እንዳሉኝና አብረን ለመሆን ቃል እንደተገባባንም ነገርኳት፡፡ ትከሻዎቿን ነቅንቃ ከማምናቸው ሰዎች ጋር ለመቆየት መወሰኔ ግሩም ብልሃት መሆኑን ነገረችኝ፡፡ በዚያ ነገሩ ሁሉ የተቋጨ መስሎኛል፤ ሆኖም ግን በቀጣዩ ቀን ይህች ሴትዮ ከጓደኞቼ ጋር በተቀመጥኩበት መጣች፡፡
‹‹ኢማኪዩሌ ጉዳዩን አስቤበታለሁ፤ ታግተኛለች ብለሽ ካሰብሽ ጓደኞችሽን ሁሉ ወደ ኪጋሊ ማምጣት ትችያለሽ፡፡ ዘጠኛችሁንም በቤቴ አስቀምጣችኋለሁ! ቢጣበብም ይመቻል፡፡››
እርስ በርሳችን ተያይተን ተሣሣቅን፡፡ እንደዚህ ያለ እንግዳና ቸርነት የሚታይበትን ስጦታ እንዴት እንደምንቀበለው አናውቅበት አልን፡፡
‹‹አስቡበት›› አለች አሎይዜ ወንበሯን እያሽከረከረች በመሄድ ላይ ሳለች፡፡ ‹‹ከጦርነቱ በኋላ ለማድረግ የምታስቡት ሌላ ምን እንዳለ አላውቅም፡፡ ሁላችሁም ተሸብራችኋል … እናንተ ልጆች እዚያች ከተማ ባለ ምርጥ ቤት ኑሩ ብዬ ልለምናችሁ መገደዴን ላምን አልችልም፡፡ ጦርነቱ እያለቀ ነው - ስለ ወደፊቱ ሕይወታችሁ ማሰብ ጀምሩ እንጂ!››
አሎይዜ ትክክል ነች፡፡ ዋና ከተማዋ በአማጽያኑ ቁጥጥር ስር ውላለች፤ ጦርነቱም ፍጻሜ ሊያገኝ የጊዜ ጉዳይ ብቻ ነው፡፡ ሁላችንም ቤተሰቦቻችንን፣ ቤታችንንና ልብሳችንን ሳይቀር ያጣን ሲሆን ከኛ መካከል አንዲት እንኳን ሳንቲም ያለው ሰው የለም፡፡ የአሎይዜን ችሮታ መቀበል ጥሩ ውሳኔ መሆኑን ለመወሰን ረጅም ጊዜ አልወሰደብንም፡፡ በማግስቱም ችሮታዋን ለመቀበልና ለማመስገን በአንድነት ሄድን፡፡
‹‹እኔን አታመስግኑኝ፤ የኢማኪዩሌን እናት እንጂ›› አለች፡፡ ‹‹ይህን የማደርገው ስለ ሮዝ እንጂ ስለ እናንተ አይደለም!››
ለራሷ መሣቅ ጀመረች፤ ከዚያም እንደገና ልባዊ የደስታ ሣቅ በምሽጉ ሙሉ እስኪያስተጋባ ድረስ ቀጠለች፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍1
#የቤተሰባችን_ፎቶ
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
አቤት የቤተሰብ ፎቶዋችን ማማሩ የጥርሳችን ንጣቱ የሣቃችን ድምቀቱ!
አባዬ እበርበት ይመስል እኔን ጥብቅ አድርጎ አቅፏል፡፡ እማዬ ይበርባት ይመስል ናሆምን ጥብቅ አድርጋ አቅፋለች፡፡ እኔና ናሆም ያለን ጥርስ ሁሉ እስኪታይ ሥቀን ከእናትና አባታችን ሥር
እንደጉልቻ ቁጭ ቁጭ ብለናል፡፡
የሚያስቀና አራት ጉልቻ፡፡ ዕዩት የእማዬን ሣቅ!
አባዬ ሚስቱን ከሚደብደብበት ቀናት በአንድ ቦክስ ሲነርታት ያወለቀው ጥርሷ የት እንደገባ እንጃ፡፡ የሚታየው እህል ነክተው የማያውቁ የሚመስሉት ነጫጭ ጥርሶቿ ብቻ ነው፡፡ ለወትሮው
ዐይኖችዋን እንደ አጥር የሚከበው ደማቅ ጥቁር ብልዝ፤ ፎቶው ላይ የለም፡፡
አባዬ ፣
“ደሞ ምን ለመሆን ነው ልጅ ከወለዱ እንዲህ ዓይነት ልብስ መልበሱ” እያለ ስለሚቆጣት፣ ብዙ ጊዜ የማትለብሰውን ፡ እጅጌው ጥሩምባ አበባን የሚመስል መዐት አበቦች የፈሰሱበት ቀሚስ ለብሳለች፡፡ ቀለሙ ዐይን የሚያደነቁር ቀይ ነው:: ከእድሜዋ ፈጥኖ
ለእርጅናና ማዲያት እጅ የሰጠው ፊትዋ በእጅ ሥራ ቆንጅቷል።
እማ ፍክት ብላለች፡፡ አበባ ነገር ሆናለች፡
አባዬን እዩትማ! ከእማዬ ጥርስ ድምቀት ጋር የሚፎካከር የወርቅ ቀለበቱ ብልጭታ፣ እጁ ላይ ትንሽ ፀሐይ ያለ አስመስሎታል። ይሄ አብረቅራቂ የጋብቻ ቀለበቱ ከማያልቀው ጭቅጨቃቸው ባንዱ ቀን፣እንዲያውም ያውልሽ! ካንቺ ጋር ያለኝ ትዳር በዚህ አብቅቷል”
ብሎ የሽንት ቤት ጉድጓድ የወረወረው ነው፡፡ እማዬ በምልጃና በልመና ጎትታ አወጣችው እንጂ!
የለበሰው ደማቅ ሮዝ ሸሚዝ፣ ከጥቁር በሮዝ መስመር መስመር
ከረቫቱ ጋር ፍጹም ተቀናጅቷል፡፡ ይሄን ከረቫት፣ ካንቺ የማያልቅ ጭቅጭቅ ለመገላገል በእዚህ ተንጠልጥዬ በሞትኩ!” እያለ እማዬን
የሚያስፈራራበትና አብዝቶ የሚለብሰው ነው፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማታ ማታ፣ ያውም በተመሳሳይ ሰዐት ፤ ትልቅ
ስልኩን ይዞ እየተንሾካሾከ ወደ ሽንትቤት ሲሮጥ ሲሮጥ ብቻ የማውቀው ሣቁ ያምራል፡፡
ናሆምዬ፣
ቀኝ እጁ ፎቶው ከመነሳቱ ሰከንዶች በፊት የተቀማውን “ሎሊፖፕ”
ሰመያዝ እንደተስተካከለ ተንከርፍፎ ቀርቷል፡፡ የአባዬን ስልክ ነካክቶ
ለእማዬ መስጠት ከጀመረ ወዲህ፣ አባዬ ሊደልለው በየቀኑ የሚገዛለትን ሎሊፖፕ
ነበር የያዘው - እማዬ ፎቶ ውስጥ አይገባም ብላ እስክትነጥቀው
ክንፍ እስከሚያካክሉት ትልልቅ ጆሮዎቹ በተዘረጋው ሰፊ ፈገግታው መሀል በቀርብ የወለቀው ጥርሱ ትቶት የሄደው ክፍተት ይታየኛል፡፡ የእማዬን ወላቃ ጥርስ በጥበቡ የደፈነው ፎቶ አንሺያችን የናሆምን መርጦ መተዉ ገረመኝ፡፡
“ይሄን ሳተላይት ጆሮ የወረስከው ከአባትህ ነው... እሱን ጠይቀው
ትለዋለች እማዬ ፤ ትምህርት ቤት በጆሮዬ ትልቅነት ሳቁብኝ ብሎ እያለቀሰ ሲነግራት፡፡ ያለችውን አምኖ አባዬን ሲጠይቅ፣ የናሆም ጆሮ የዘር ግንድ፣ አዲስ የጭቅጭቅ ማገዶ ይሆናል፡፡ እነሱ
በጩኸት ሲጨቃጨቁ የሳሎኑን ጥግ ይዞ ሲያለቅስ የማየው ልብ ሰባሪ ፊቱ እዚህ የለም፡፡
እኔ፣
አርቴፊሻል ፈገግታዬ ለፊቴ እንግዳ የሆነበት አይመስልም፡፡ ጥርሴ
እንኳን፣ ከዓመት ጀምሮ ከትምህርት ቤታችን ሦስት አጥር ዘልሎ
ካለው መርኬ ጫት ቤት እየሄድኩ፤ ከብዙ ጎረምሶች ጋር ታጅዬ ጫት ሳሻምድና ሺሻ ሳጨስ እንደምውል አያሳብቅም፡፡
አገጬን ሊነካ ምንም ያልቀረው ቢትልስ ሹራቤ ትላንት መርኬ ጓዳ፣ ጥግ ካለው ፍራሽ ላይ፣ የሰሞኑ ጓደኛዬ መሳይ በአንገቱ ላይ የሰራውን የገድል ማስታወሻ ሸፍኖታል፡፡
አቀማመጤ እንደጨዋ ልጃገረድ ሰብሰብ፣ ቆጠብ ! ከረጅም ቀሚሴ ጋር የሚሄድ ነው፡፡ አባዬ፣ ድሮ ሁሉ ነገር እነግረው በነበረ ጊዜ ያቅፈኝ እንደነበረው ስላቀፈኝ፤ ከአስተቃቀፉ ጋር የድሮን
ንጽሕናዬን ለማምጣት ባደረግኩት ከፍተኛ ጥረት ያመጣሁት
አቀማመጥ አይመስልም፡፡
ያቀፈኝ እጁን አያያዜ፣ ጥብቅ ያለና አትልቀቀኝ የሚል ይመስላል፡፡
“አባዬ መልሰኝ... አባዬ ልጠፋ ነው መልሰኝ” የሚል፡፡ ከቤታችን
ሰላም ጋር አብሮ የጠፋው ጨዋነቴን በአባቴ እቅፍ ውስጥ እፈልግ
ይመስል የምለምነው ይመስላል፡፡
...አቤት የቤተሰብ ፎቶዋችን ማማሩ! የጥርሳችን ንጣቱ! የሣቃችን ድምቀቱ!
.
የምፈልገው ቤተሰብ ፎቶዋችን ላይ ያለውን ነው፡፡
የምመኘው ቤተሰብ ፎቶዋችን ላይ ያለውን ነው፡፡
አሁን አሁን የምጸልየው፤ ፎቶው ላይ እንዳለው ያለ ቤተሰብ
እንዲሰጠኝ ብቻ ነው፡፡
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ቀን። 🙏
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
፡
አቤት የቤተሰብ ፎቶዋችን ማማሩ የጥርሳችን ንጣቱ የሣቃችን ድምቀቱ!
አባዬ እበርበት ይመስል እኔን ጥብቅ አድርጎ አቅፏል፡፡ እማዬ ይበርባት ይመስል ናሆምን ጥብቅ አድርጋ አቅፋለች፡፡ እኔና ናሆም ያለን ጥርስ ሁሉ እስኪታይ ሥቀን ከእናትና አባታችን ሥር
እንደጉልቻ ቁጭ ቁጭ ብለናል፡፡
የሚያስቀና አራት ጉልቻ፡፡ ዕዩት የእማዬን ሣቅ!
አባዬ ሚስቱን ከሚደብደብበት ቀናት በአንድ ቦክስ ሲነርታት ያወለቀው ጥርሷ የት እንደገባ እንጃ፡፡ የሚታየው እህል ነክተው የማያውቁ የሚመስሉት ነጫጭ ጥርሶቿ ብቻ ነው፡፡ ለወትሮው
ዐይኖችዋን እንደ አጥር የሚከበው ደማቅ ጥቁር ብልዝ፤ ፎቶው ላይ የለም፡፡
አባዬ ፣
“ደሞ ምን ለመሆን ነው ልጅ ከወለዱ እንዲህ ዓይነት ልብስ መልበሱ” እያለ ስለሚቆጣት፣ ብዙ ጊዜ የማትለብሰውን ፡ እጅጌው ጥሩምባ አበባን የሚመስል መዐት አበቦች የፈሰሱበት ቀሚስ ለብሳለች፡፡ ቀለሙ ዐይን የሚያደነቁር ቀይ ነው:: ከእድሜዋ ፈጥኖ
ለእርጅናና ማዲያት እጅ የሰጠው ፊትዋ በእጅ ሥራ ቆንጅቷል።
እማ ፍክት ብላለች፡፡ አበባ ነገር ሆናለች፡
አባዬን እዩትማ! ከእማዬ ጥርስ ድምቀት ጋር የሚፎካከር የወርቅ ቀለበቱ ብልጭታ፣ እጁ ላይ ትንሽ ፀሐይ ያለ አስመስሎታል። ይሄ አብረቅራቂ የጋብቻ ቀለበቱ ከማያልቀው ጭቅጨቃቸው ባንዱ ቀን፣እንዲያውም ያውልሽ! ካንቺ ጋር ያለኝ ትዳር በዚህ አብቅቷል”
ብሎ የሽንት ቤት ጉድጓድ የወረወረው ነው፡፡ እማዬ በምልጃና በልመና ጎትታ አወጣችው እንጂ!
የለበሰው ደማቅ ሮዝ ሸሚዝ፣ ከጥቁር በሮዝ መስመር መስመር
ከረቫቱ ጋር ፍጹም ተቀናጅቷል፡፡ ይሄን ከረቫት፣ ካንቺ የማያልቅ ጭቅጭቅ ለመገላገል በእዚህ ተንጠልጥዬ በሞትኩ!” እያለ እማዬን
የሚያስፈራራበትና አብዝቶ የሚለብሰው ነው፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማታ ማታ፣ ያውም በተመሳሳይ ሰዐት ፤ ትልቅ
ስልኩን ይዞ እየተንሾካሾከ ወደ ሽንትቤት ሲሮጥ ሲሮጥ ብቻ የማውቀው ሣቁ ያምራል፡፡
ናሆምዬ፣
ቀኝ እጁ ፎቶው ከመነሳቱ ሰከንዶች በፊት የተቀማውን “ሎሊፖፕ”
ሰመያዝ እንደተስተካከለ ተንከርፍፎ ቀርቷል፡፡ የአባዬን ስልክ ነካክቶ
ለእማዬ መስጠት ከጀመረ ወዲህ፣ አባዬ ሊደልለው በየቀኑ የሚገዛለትን ሎሊፖፕ
ነበር የያዘው - እማዬ ፎቶ ውስጥ አይገባም ብላ እስክትነጥቀው
ክንፍ እስከሚያካክሉት ትልልቅ ጆሮዎቹ በተዘረጋው ሰፊ ፈገግታው መሀል በቀርብ የወለቀው ጥርሱ ትቶት የሄደው ክፍተት ይታየኛል፡፡ የእማዬን ወላቃ ጥርስ በጥበቡ የደፈነው ፎቶ አንሺያችን የናሆምን መርጦ መተዉ ገረመኝ፡፡
“ይሄን ሳተላይት ጆሮ የወረስከው ከአባትህ ነው... እሱን ጠይቀው
ትለዋለች እማዬ ፤ ትምህርት ቤት በጆሮዬ ትልቅነት ሳቁብኝ ብሎ እያለቀሰ ሲነግራት፡፡ ያለችውን አምኖ አባዬን ሲጠይቅ፣ የናሆም ጆሮ የዘር ግንድ፣ አዲስ የጭቅጭቅ ማገዶ ይሆናል፡፡ እነሱ
በጩኸት ሲጨቃጨቁ የሳሎኑን ጥግ ይዞ ሲያለቅስ የማየው ልብ ሰባሪ ፊቱ እዚህ የለም፡፡
እኔ፣
አርቴፊሻል ፈገግታዬ ለፊቴ እንግዳ የሆነበት አይመስልም፡፡ ጥርሴ
እንኳን፣ ከዓመት ጀምሮ ከትምህርት ቤታችን ሦስት አጥር ዘልሎ
ካለው መርኬ ጫት ቤት እየሄድኩ፤ ከብዙ ጎረምሶች ጋር ታጅዬ ጫት ሳሻምድና ሺሻ ሳጨስ እንደምውል አያሳብቅም፡፡
አገጬን ሊነካ ምንም ያልቀረው ቢትልስ ሹራቤ ትላንት መርኬ ጓዳ፣ ጥግ ካለው ፍራሽ ላይ፣ የሰሞኑ ጓደኛዬ መሳይ በአንገቱ ላይ የሰራውን የገድል ማስታወሻ ሸፍኖታል፡፡
አቀማመጤ እንደጨዋ ልጃገረድ ሰብሰብ፣ ቆጠብ ! ከረጅም ቀሚሴ ጋር የሚሄድ ነው፡፡ አባዬ፣ ድሮ ሁሉ ነገር እነግረው በነበረ ጊዜ ያቅፈኝ እንደነበረው ስላቀፈኝ፤ ከአስተቃቀፉ ጋር የድሮን
ንጽሕናዬን ለማምጣት ባደረግኩት ከፍተኛ ጥረት ያመጣሁት
አቀማመጥ አይመስልም፡፡
ያቀፈኝ እጁን አያያዜ፣ ጥብቅ ያለና አትልቀቀኝ የሚል ይመስላል፡፡
“አባዬ መልሰኝ... አባዬ ልጠፋ ነው መልሰኝ” የሚል፡፡ ከቤታችን
ሰላም ጋር አብሮ የጠፋው ጨዋነቴን በአባቴ እቅፍ ውስጥ እፈልግ
ይመስል የምለምነው ይመስላል፡፡
...አቤት የቤተሰብ ፎቶዋችን ማማሩ! የጥርሳችን ንጣቱ! የሣቃችን ድምቀቱ!
.
የምፈልገው ቤተሰብ ፎቶዋችን ላይ ያለውን ነው፡፡
የምመኘው ቤተሰብ ፎቶዋችን ላይ ያለውን ነው፡፡
አሁን አሁን የምጸልየው፤ ፎቶው ላይ እንዳለው ያለ ቤተሰብ
እንዲሰጠኝ ብቻ ነው፡፡
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ቀን። 🙏
🥰1
#ሁቱትሲ
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_አምስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ወደ_አማጽያኑ_የሚወስደው_መንገድ
፡
፡
በነሃሴ መጨረሻ በአንድ ሞቃት ከሰዓት በኋላ የፈረንሳዩ መኰንን ምሽጉን ለቀን ልንሄድ እንደሆነ ነገረኝ፡፡ ዘመቻ ቱርኮይዝ ተጠናቀቀ፣ ስለሆነም ፈረንሳውያኑ ከሩዋንዳ ለመውጣት ይዘገጃጃሉ፡፡ ‹‹ምሽጋችንን ዛሬ እንዘጋለን›› አለኝ፡፡ ‹‹በሁለት ሰዓታት ውስጥ ሁሉም ሰው ይህን ምሽግ ለቆ እንዲወጣ ይዘገጃጅ፡፡››
‹‹የት ነው የምንሄደው?›› ስል ጠየቅሁት፡፡ ‹‹እዚህ ሰላሳ ሰዎች አሉ… የት ሂዱ ልበላቸው? ቤት የለንም!›› በድንገተኛው ዜና ተገረምኩ፡፡
‹‹ሁላችሁንም ከቱትሲ ወታደሮች ጋር እንድትቆዩ ልንወስዳችሁ ነው፡፡ ሩአግ ወደ አካባቢው የተጠጋ ሲሆን ካለንበት ስፍራ የተወሰኑ ኪሎሜትሮች ራቅ ብሎም ምሽግ
አቋቁሟል፡፡ እዚያ ወስደን ለእነርሱ እንሰጣችኋለን፡፡ ከራሳችሁ ሰዎች ጋር መሆኑ ይሻላችኋል፡፡››
የቱትሲ ወታደሮቹ በመጨረሻ ወደኛ እየተዋጉ መምጣታቸውንና ኢንተርሃምዌዎችን ከሀገር እያስወጡ መሆናቸውን በመስማቴ ተደሰትኩ፡፡ ጀግናችን፣ የሩአጉ መሪ ፖል ካጋሜ፣ በኪጋሊ አዲስ መንግሥት ማቋቋሙን ሳይቀር ሰማሁ፡፡ እግዚአብሔር ይመስገን በመጨረሻም ሰላም አገኘን - ያች ቀን ደረሰች፤ የዘር ጭፍጨፋው መቆሙ ነው!
መሄዳችን መሆኑን በምሽጉ እየተዘዋወርኩ ለእያንዳንዱ ሰው ተናገርኩ፡፡ በቅርቡ ከመጡት አንዳንዶቹ ተጠራጠሩ፤ ፈረንሳውያኑ የማይታመኑና የስደተኛ መጠለያውን ያዘጋጁትም የዘር ጭፍጨፋውን ያስተባበሩትን ሁቱዎች በኪቩ ሐይቅ የማሻገርና ከሩዋንዳ በደኅና የማስወጣት እውነተኛ ተልዕኳቸውን ለመሸፈን እንደ ሰብዓዊ መከላከያ አድርገው ለመጠቀም ነው ሲሉ ተናገሩ፡፡
‹‹ይህን እንኳን አላምንም›› አልኳቸው፡፡ ‹‹ፈረንሳውያኑ ለሳምንታት በደኅና ይዘውን ከርመዋል፤ ነጻ ሊያወጡንም ትንሽ ነው የቀራቸው! እናደርጋለን ያሉትን ሁሉ እያደረጉልን ነው፡፡››
በተጠንቀቅ ስለሆንን ለመዘገጃጀት ጊዜ አልወሰደብንም፡፡ ጓዝ ብሎ ነገር ያለው ስደተኛ የለም፡፡ በመሆኑም የምንሸክፈው ኮተት የለንም፡፡ ያሉኝን ጥቂት ንብረቶች ሰባሰብኩ - የቄስ ሙሪንዚ ልጅ የሰጠችኝን ሹራቤንና ፎጣዬን፣ ፒየር የሰጠኝን ሁለት መጻሕፍትና የተወሰኑ ወታደሮቹ የሰጡኝን ትርፍ ሳሙናዎችና ቲሸርቶችን በከረጢት አደረግሁ፡፡ ይህን ሳደርግ ግን እናቴ ገዳዮቹ በቤታችን አካባቢ እንደተሰበሰቡ እቃዎቿን በሻንጣዎች ስትከት የነበረው ትዝ አለኝና ካለፈው ሕይወቴ እቃዎችን ወደ አዲሱ ሕይወቴ ማንኳተት እንደሌለብኝ ወሰንኩ፡፡ በሁለቱ ሕይወቶቼ መካከል ንጹሕ መለያያ ለማድረግ ወሰንኩ፡፡ ከረጢቱን አንድ ሌላ ምስኪን ቤት-አልባ ቱትሲ ያገኘው ዘንድ በመመኘት ወደ መማሪያ ክፍሉ ወስጄ ጥጋት ላይ ተውኩት፡፡ ልሄድ ዘወር ስል በሩ ላይ ከቆመው ከፒየር ጋር ድንገት ግጥምጥም አልን፡፡ በሐዘኔታ አየኝና አንዲት ወረቀት ሰጠኝ፡፡ ‹‹እንዲያው ምናልባት ሐሳብሽን ከቀየርሽ ይህ የፈረንሳዩ አድራሻዬ ነው፡፡ በጣም እናፍቅሻለሁ፤ በልቤም አኖርሻለሁ፡፡ አምላክ በደኅና እንዲያቆይሽ እጸልያለሁ፡፡››
‹‹በል ደኅና ሁን ፒየር፡፡ እግዚአብሔር ይባርክህ›› ብልም እርሱ ግን ምላሼን እንኳን ሳይሰማ ሄዶ ኖሯል፡፡
በተሸከርካሪው ኋላ ላይ ለመውጣት የመጨረሻዋ ነኝ፡፡ የኋላ መዝጊያው ገጭ ብሎ ሲዘጋ የሸራ ከለላው እኛን ለመደበቅ ቁልቁል ተጋረደ፤ ተሽከርካሪውም ወደፊት ተንቀሳቀሰ፡፡ መቼም አሳልፌ የማልሰጠው ንብረቴን፣ አባቴ የሰጠኝን መቁጠሪያዬን፣ አወጣሁና ጸሎቴን አደረስኩበት፡፡ እግዚአብሔርን በአዲሱ መንገዳችን እንዲባርከንና ወደ ቱትሲ ወታደሮቹ በደኅና እንዲያደርሰን ጠየቅሁት፡፡
ተሸከርካሪው በግማሽ ክብ ቅርጽ የተደረደሩትን ብረት-ለበስ ተሸከርካሪዎችና ቁልቁል ጥርጊያ መንገዱን አልፎ ወደ ገዳዮች ባሕር ሰጠመ! ሸራው ላይ ባለች ትንሽ ቀዳዳ አጮልቄ በሺዎች የሚቆጠሩ ሁቱዎች በዋናው መንገድ ወደ ኪቩ ሐይቅ ሲተሙ አየሁ - ከመካከላቸው በመቶዎች የሚቆጠሩት የኢንተርሃምዌን የደንብ ልብስ ለብሰው ገጀራ ይዘዋል፡፡
‹‹ወይ አምላኬ›› አልኩ ተሸከርካሪው ላይ እንደገና ወድቄ፡፡ ‹‹ድጋሚ አያምጣው!›› ሁቱዎቹ መንገድ እንዲለቁና እንዲያሳልፉን የተሸከርካሪውን ጡሩንባ እየነፋን በተጨናነቀው መንገድ እናዘግም ገባን፡፡ ኢንተርሃምዌዎቹ ካስቆሙን ወይም ተሸከርካሪያችን ከተበላሸ በደቂቃዎች ውስጥ ይረባረቡብናል፡፡ መታጠቢያ ቤቱን ለቅቄ ከወጣሁ ወዲህ ይህን ያህል ፈርቼ አላውቅም፡፡
‹‹እባክህ አምላኬ›› ስል ጸለይኩ፡፡ ‹‹ይህን ያህል አምጥተኸናል - አሁን ቀሪውንም ጎዳና ውሰደን! እነዚህን ገዳዮችም አሳውርልን … እዚህ ተሸከርካሪ ጀርባ ላይ እንዲያዩ አታድርጋቸው፡፡ መሐሪው ጌታ ሆይ! ከነዚህ ጥላቻ ከተሞላባቸው ዓይኖቻቸው ሰውረን!››
ወደ ሩአግ ምሽግ ከሚወስደን መንገዳችን ከግማሽ በላይ እንደሄድን ተሸከርካሪው ቆመ፡፡ ፈረንሳዊው መኰንን ወደ ኋላ መጥቶ ሸራውን ገለጠና ‹‹በአካባቢው ተኩስ አለ የሚል ወሬ ደርሶናል፤ ስለሆነም በማናቸውም ሁኔታ ቢሆን ተኩስን የማስቆም ግዴታ አለብን፡፡ ስለዚህ ልንመለስ ስለሆነ የግድ እዚህ መውረድ አለባችሁ፡፡›› አሳስቼ የሰማሁት መሰለኝ፡፡ ‹‹መልሰህ ትወስደናለህ ማለት ነው፣ አይደል?››
‹‹አይ፣ መጠለያውን ልንዘጋው ስለሆነ ብትመለሱም የምታርፉበት ስፍራ የለም፡፡ እዚህ መውረድ አለባችሁ… አሁኑኑ፡፡ ይቅርታ እንግዲህ ኢማኪዩሌ፡፡›› ባለፉት ጥቂት ሳምንታት መኰንኑን በደንብ አውቄዋለሁ፡፡ ሁቱ ገዳዮችን ስለሚጠላ ቱትሲዎችን በተቻለው መጠን ለመርዳት እንደሚፈልግ ተናግሯል፤ ስለሆነም በታጠቁ ኢንተርሃምዌዎች እጅ ሊጥለን ነው ብዬ ላምን አልቻልኩም፡፡ እርሱን ለማሳመን ከተሽከርካሪው ወረድኩ፡፡ ‹‹እባክህ፣ መኰንን ሆይ፣ እዚህ ከተውከን ምን እንደሚከሰትብን ከማንም በላይ ታውቃለህ፡፡ በዙሪያችን ገዳዮቹ እያንዣበቡ ነው! እባክህ ተለመነኝ … የሩአግ ምሽግ ከዚህ በኋላ ግፋ ቢል አንድ ኪሎሜትር ስለሚርቅ እባክህ እዚያ አድርሰን፤ አሊያም መልሰህ ውሰደን … እዚህ ለእርድ አትተወን!››
‹‹ይቅርታ ኢማኪዩሌ፡፡ ትዕዛዝ አለብኝ፡፡››
‹‹እባክህ መኰንን ብትወስደን ምናለ!››
‹‹አይ! ሰዎችሽን አውርጅልኝ፡፡ መሄድ አለብን፡፡››
አንድ ደርዘን ገደማ ኢንተርሃምዌዎች አሥር ጫማ በሚሆን ርቀት እየተከታተሉን፣ የምንነጋገረውን እየሰሙና ፍላጎታቸው በጣም አይሎ ስለቆሙ እየተከሰተ ያለውን ነገር ልናምን አልቻልንም፡፡ ጨነቀኝ፤ መሬቷም ዞረችብኝ፣ ለአንድ አፍታ እንኳን የማየው ነገር የቁጡ ፊቶችን ብዥታ ሆነ፡፡ ራሴን በተሸከርካሪው አንድ ጎን ላይ አረጋግቼ ቆሜ ለመጀመሪያ ጊዜ በመሬት ላይ ያሉትን አስከሬኖች ምንነት አወቅሁ - መንገዱን ተከትሎ ዓይኔ እስከሚያየው ድረስ ሳማትር አስከሬኖች በየቦታው ወድቀዋል፡፡
መኰንኑን ቀና ብዬ አይቼ በዓይኖቼ ለመጨረሻ ጊዜ ተለማመጥኩት፡፡ ረብ-አልባ ነው - ወይ ፍንክች አለ፡፡ ምናልባት ቄሱና ሌሎቹ ስለ ፈረንሳውያኑ የተናገሩት ልክ ነው ማለት ነው፡፡ እውነት እዚህ የመጡት ገዳዮቹን ለመርዳት ይሆን? ይኸው በእርግጠኝነት ለሞት ሊተዉን ነው፡፡
ለጓደኞቼ ‹‹ኑ ውረዱ›› አልኳቸው፡፡ ‹‹ሁላችሁም ውረዱ … ፈረንጆቹ እዚህ ትተውን ሊሄዱ ነው፡፡››
፡
፡
#ምዕራፍ_አስራ_አምስት
፡
፡
#የወጣቷ_ልብ_አንጠልጣይ_ትውስታዎች
፡
#ትርጉም_በመዝምር_ግርማ
፡
፡
#ወደ_አማጽያኑ_የሚወስደው_መንገድ
፡
፡
በነሃሴ መጨረሻ በአንድ ሞቃት ከሰዓት በኋላ የፈረንሳዩ መኰንን ምሽጉን ለቀን ልንሄድ እንደሆነ ነገረኝ፡፡ ዘመቻ ቱርኮይዝ ተጠናቀቀ፣ ስለሆነም ፈረንሳውያኑ ከሩዋንዳ ለመውጣት ይዘገጃጃሉ፡፡ ‹‹ምሽጋችንን ዛሬ እንዘጋለን›› አለኝ፡፡ ‹‹በሁለት ሰዓታት ውስጥ ሁሉም ሰው ይህን ምሽግ ለቆ እንዲወጣ ይዘገጃጅ፡፡››
‹‹የት ነው የምንሄደው?›› ስል ጠየቅሁት፡፡ ‹‹እዚህ ሰላሳ ሰዎች አሉ… የት ሂዱ ልበላቸው? ቤት የለንም!›› በድንገተኛው ዜና ተገረምኩ፡፡
‹‹ሁላችሁንም ከቱትሲ ወታደሮች ጋር እንድትቆዩ ልንወስዳችሁ ነው፡፡ ሩአግ ወደ አካባቢው የተጠጋ ሲሆን ካለንበት ስፍራ የተወሰኑ ኪሎሜትሮች ራቅ ብሎም ምሽግ
አቋቁሟል፡፡ እዚያ ወስደን ለእነርሱ እንሰጣችኋለን፡፡ ከራሳችሁ ሰዎች ጋር መሆኑ ይሻላችኋል፡፡››
የቱትሲ ወታደሮቹ በመጨረሻ ወደኛ እየተዋጉ መምጣታቸውንና ኢንተርሃምዌዎችን ከሀገር እያስወጡ መሆናቸውን በመስማቴ ተደሰትኩ፡፡ ጀግናችን፣ የሩአጉ መሪ ፖል ካጋሜ፣ በኪጋሊ አዲስ መንግሥት ማቋቋሙን ሳይቀር ሰማሁ፡፡ እግዚአብሔር ይመስገን በመጨረሻም ሰላም አገኘን - ያች ቀን ደረሰች፤ የዘር ጭፍጨፋው መቆሙ ነው!
መሄዳችን መሆኑን በምሽጉ እየተዘዋወርኩ ለእያንዳንዱ ሰው ተናገርኩ፡፡ በቅርቡ ከመጡት አንዳንዶቹ ተጠራጠሩ፤ ፈረንሳውያኑ የማይታመኑና የስደተኛ መጠለያውን ያዘጋጁትም የዘር ጭፍጨፋውን ያስተባበሩትን ሁቱዎች በኪቩ ሐይቅ የማሻገርና ከሩዋንዳ በደኅና የማስወጣት እውነተኛ ተልዕኳቸውን ለመሸፈን እንደ ሰብዓዊ መከላከያ አድርገው ለመጠቀም ነው ሲሉ ተናገሩ፡፡
‹‹ይህን እንኳን አላምንም›› አልኳቸው፡፡ ‹‹ፈረንሳውያኑ ለሳምንታት በደኅና ይዘውን ከርመዋል፤ ነጻ ሊያወጡንም ትንሽ ነው የቀራቸው! እናደርጋለን ያሉትን ሁሉ እያደረጉልን ነው፡፡››
በተጠንቀቅ ስለሆንን ለመዘገጃጀት ጊዜ አልወሰደብንም፡፡ ጓዝ ብሎ ነገር ያለው ስደተኛ የለም፡፡ በመሆኑም የምንሸክፈው ኮተት የለንም፡፡ ያሉኝን ጥቂት ንብረቶች ሰባሰብኩ - የቄስ ሙሪንዚ ልጅ የሰጠችኝን ሹራቤንና ፎጣዬን፣ ፒየር የሰጠኝን ሁለት መጻሕፍትና የተወሰኑ ወታደሮቹ የሰጡኝን ትርፍ ሳሙናዎችና ቲሸርቶችን በከረጢት አደረግሁ፡፡ ይህን ሳደርግ ግን እናቴ ገዳዮቹ በቤታችን አካባቢ እንደተሰበሰቡ እቃዎቿን በሻንጣዎች ስትከት የነበረው ትዝ አለኝና ካለፈው ሕይወቴ እቃዎችን ወደ አዲሱ ሕይወቴ ማንኳተት እንደሌለብኝ ወሰንኩ፡፡ በሁለቱ ሕይወቶቼ መካከል ንጹሕ መለያያ ለማድረግ ወሰንኩ፡፡ ከረጢቱን አንድ ሌላ ምስኪን ቤት-አልባ ቱትሲ ያገኘው ዘንድ በመመኘት ወደ መማሪያ ክፍሉ ወስጄ ጥጋት ላይ ተውኩት፡፡ ልሄድ ዘወር ስል በሩ ላይ ከቆመው ከፒየር ጋር ድንገት ግጥምጥም አልን፡፡ በሐዘኔታ አየኝና አንዲት ወረቀት ሰጠኝ፡፡ ‹‹እንዲያው ምናልባት ሐሳብሽን ከቀየርሽ ይህ የፈረንሳዩ አድራሻዬ ነው፡፡ በጣም እናፍቅሻለሁ፤ በልቤም አኖርሻለሁ፡፡ አምላክ በደኅና እንዲያቆይሽ እጸልያለሁ፡፡››
‹‹በል ደኅና ሁን ፒየር፡፡ እግዚአብሔር ይባርክህ›› ብልም እርሱ ግን ምላሼን እንኳን ሳይሰማ ሄዶ ኖሯል፡፡
በተሸከርካሪው ኋላ ላይ ለመውጣት የመጨረሻዋ ነኝ፡፡ የኋላ መዝጊያው ገጭ ብሎ ሲዘጋ የሸራ ከለላው እኛን ለመደበቅ ቁልቁል ተጋረደ፤ ተሽከርካሪውም ወደፊት ተንቀሳቀሰ፡፡ መቼም አሳልፌ የማልሰጠው ንብረቴን፣ አባቴ የሰጠኝን መቁጠሪያዬን፣ አወጣሁና ጸሎቴን አደረስኩበት፡፡ እግዚአብሔርን በአዲሱ መንገዳችን እንዲባርከንና ወደ ቱትሲ ወታደሮቹ በደኅና እንዲያደርሰን ጠየቅሁት፡፡
ተሸከርካሪው በግማሽ ክብ ቅርጽ የተደረደሩትን ብረት-ለበስ ተሸከርካሪዎችና ቁልቁል ጥርጊያ መንገዱን አልፎ ወደ ገዳዮች ባሕር ሰጠመ! ሸራው ላይ ባለች ትንሽ ቀዳዳ አጮልቄ በሺዎች የሚቆጠሩ ሁቱዎች በዋናው መንገድ ወደ ኪቩ ሐይቅ ሲተሙ አየሁ - ከመካከላቸው በመቶዎች የሚቆጠሩት የኢንተርሃምዌን የደንብ ልብስ ለብሰው ገጀራ ይዘዋል፡፡
‹‹ወይ አምላኬ›› አልኩ ተሸከርካሪው ላይ እንደገና ወድቄ፡፡ ‹‹ድጋሚ አያምጣው!›› ሁቱዎቹ መንገድ እንዲለቁና እንዲያሳልፉን የተሸከርካሪውን ጡሩንባ እየነፋን በተጨናነቀው መንገድ እናዘግም ገባን፡፡ ኢንተርሃምዌዎቹ ካስቆሙን ወይም ተሸከርካሪያችን ከተበላሸ በደቂቃዎች ውስጥ ይረባረቡብናል፡፡ መታጠቢያ ቤቱን ለቅቄ ከወጣሁ ወዲህ ይህን ያህል ፈርቼ አላውቅም፡፡
‹‹እባክህ አምላኬ›› ስል ጸለይኩ፡፡ ‹‹ይህን ያህል አምጥተኸናል - አሁን ቀሪውንም ጎዳና ውሰደን! እነዚህን ገዳዮችም አሳውርልን … እዚህ ተሸከርካሪ ጀርባ ላይ እንዲያዩ አታድርጋቸው፡፡ መሐሪው ጌታ ሆይ! ከነዚህ ጥላቻ ከተሞላባቸው ዓይኖቻቸው ሰውረን!››
ወደ ሩአግ ምሽግ ከሚወስደን መንገዳችን ከግማሽ በላይ እንደሄድን ተሸከርካሪው ቆመ፡፡ ፈረንሳዊው መኰንን ወደ ኋላ መጥቶ ሸራውን ገለጠና ‹‹በአካባቢው ተኩስ አለ የሚል ወሬ ደርሶናል፤ ስለሆነም በማናቸውም ሁኔታ ቢሆን ተኩስን የማስቆም ግዴታ አለብን፡፡ ስለዚህ ልንመለስ ስለሆነ የግድ እዚህ መውረድ አለባችሁ፡፡›› አሳስቼ የሰማሁት መሰለኝ፡፡ ‹‹መልሰህ ትወስደናለህ ማለት ነው፣ አይደል?››
‹‹አይ፣ መጠለያውን ልንዘጋው ስለሆነ ብትመለሱም የምታርፉበት ስፍራ የለም፡፡ እዚህ መውረድ አለባችሁ… አሁኑኑ፡፡ ይቅርታ እንግዲህ ኢማኪዩሌ፡፡›› ባለፉት ጥቂት ሳምንታት መኰንኑን በደንብ አውቄዋለሁ፡፡ ሁቱ ገዳዮችን ስለሚጠላ ቱትሲዎችን በተቻለው መጠን ለመርዳት እንደሚፈልግ ተናግሯል፤ ስለሆነም በታጠቁ ኢንተርሃምዌዎች እጅ ሊጥለን ነው ብዬ ላምን አልቻልኩም፡፡ እርሱን ለማሳመን ከተሽከርካሪው ወረድኩ፡፡ ‹‹እባክህ፣ መኰንን ሆይ፣ እዚህ ከተውከን ምን እንደሚከሰትብን ከማንም በላይ ታውቃለህ፡፡ በዙሪያችን ገዳዮቹ እያንዣበቡ ነው! እባክህ ተለመነኝ … የሩአግ ምሽግ ከዚህ በኋላ ግፋ ቢል አንድ ኪሎሜትር ስለሚርቅ እባክህ እዚያ አድርሰን፤ አሊያም መልሰህ ውሰደን … እዚህ ለእርድ አትተወን!››
‹‹ይቅርታ ኢማኪዩሌ፡፡ ትዕዛዝ አለብኝ፡፡››
‹‹እባክህ መኰንን ብትወስደን ምናለ!››
‹‹አይ! ሰዎችሽን አውርጅልኝ፡፡ መሄድ አለብን፡፡››
አንድ ደርዘን ገደማ ኢንተርሃምዌዎች አሥር ጫማ በሚሆን ርቀት እየተከታተሉን፣ የምንነጋገረውን እየሰሙና ፍላጎታቸው በጣም አይሎ ስለቆሙ እየተከሰተ ያለውን ነገር ልናምን አልቻልንም፡፡ ጨነቀኝ፤ መሬቷም ዞረችብኝ፣ ለአንድ አፍታ እንኳን የማየው ነገር የቁጡ ፊቶችን ብዥታ ሆነ፡፡ ራሴን በተሸከርካሪው አንድ ጎን ላይ አረጋግቼ ቆሜ ለመጀመሪያ ጊዜ በመሬት ላይ ያሉትን አስከሬኖች ምንነት አወቅሁ - መንገዱን ተከትሎ ዓይኔ እስከሚያየው ድረስ ሳማትር አስከሬኖች በየቦታው ወድቀዋል፡፡
መኰንኑን ቀና ብዬ አይቼ በዓይኖቼ ለመጨረሻ ጊዜ ተለማመጥኩት፡፡ ረብ-አልባ ነው - ወይ ፍንክች አለ፡፡ ምናልባት ቄሱና ሌሎቹ ስለ ፈረንሳውያኑ የተናገሩት ልክ ነው ማለት ነው፡፡ እውነት እዚህ የመጡት ገዳዮቹን ለመርዳት ይሆን? ይኸው በእርግጠኝነት ለሞት ሊተዉን ነው፡፡
ለጓደኞቼ ‹‹ኑ ውረዱ›› አልኳቸው፡፡ ‹‹ሁላችሁም ውረዱ … ፈረንጆቹ እዚህ ትተውን ሊሄዱ ነው፡፡››
ከተሸከርካሪው ጀርባ የሚመጡት ያለማመንና የፍርሃት ጩኸቶች እየቀረቡን የመጡትን ገዳዮች ትኩረት የበለጠ ሳቡ፡፡ አንዱን ኢንተርሃምዌ ዓይኑን ትኩር ብዬ አይቼ አትኩሮቱን ያዝኩበት፡፡ እንደኔ ዓይነት ሰው እንደሆነና በእውነት መግደል እንዳልፈለገ ልቤ ነግሮኛል፡፡ መቁጠሪያዬን ይዤ ለእርሱ የፍቅር መልዕክት ለመላክ ቁርጠኝነቴን ሁሉ ሰበሰብኩት፡፡ አምላክ ገዳዩን በፍቅሩ ኃይል እንድዳስሰው እንዲጠቀምብኝ ጸለይኩ፡፡
ዓይኖቼን አልጨፈንኳቸውም … እናም ያንድ ሰው ዕድሜ ለመሰለኝ ያህል ጊዜ ተፋጠጥን፡፡ በመጨረሻም ገዳዩ ሳፈጥበት እይታውን ወደ ሌላ አቅጣጫ አዞረ፡፡ ሰይጣን ሰውነቱን ትቶት እንደሄደ ሁሉ ጀርባውን አዙሮ ገጀራውን አሽቀንጥሮ ጣለው፡፡ በአንጻሩ ሌሎች ብዙ ዲያብሎሶች የእርሱን ስፍራ ለመተካት ተዘጋጅተዋል፡፡ ቢያንስ 15 ኢንተርሃምዌዎች ከተሸከርካሪው የተወሰኑ እርምጃዎች ርቀት ላይ ገጀራ ይዘው ፊታቸውን ተኮሳትረው ቆመዋል፤ እየተከሰተ ያለውን ነገር ምንነት በማጤን ከጓደኞቼ አንዳቸው እንኳን ለመውረድ አለመድፈራቸውን ያዩ ይዘዋል፡፡ ከመውጣት ውጪ ምንም አማራጭ የለንም፡፡ ሰላሳችንም እዚያ ገዳዮቹን ተጋፍጠን እስክንቆም ድረስ ጓደኞቼ አንድ በአንድ እየዘለሉ ወረዱ፡፡ ሁሉም ወርዶ እንዳለቀ ሁለት የፈረንሳይ ወታደሮች አሎይዜን አወረዷት፤ ልጆቿንም ኬንዛንና ሳሚን ከጎኗ አደረጉላት፡፡ ወታደሮቹ ተሳፈሩና ተሽከርካሪው በአቧራና እርግጠኝነት እጦት ደመና ውስጥ ትቶን በከፍተኛ ፍጥነት ነጎደ፡፡
አንደኛው ገዳይ ‹‹እነዚህን ሁሉ ቱትሲዎች እዩዋቸው›› ሲል በመገረም ተናገረ፡፡ ‹‹እንዴት ነው እስካሁን በሕይወት ሊኖሩ የቻሉት?››
‹‹የፈረንሳይ ወታደሮች ከለላ ሰጥተዋቸው የነበሩት በረሮዎች ናቸው›› አለ ሌላኛው፡፡ ‹‹እስኪ አሁን ማነው የሚያድናችሁ? በረሮ ሁላ!››
ጓደኞቼ በጣም ስለፈሩ መንቀሳቀስ እንኳን ተሳናቸው፡፡ ለጨካኝ ገዳዮች መላ በመዘየድ ባለሙያ የሆንኩ ይመስል ጎሰም አድርገው ምን ማድረግ እንደሚገባን ጠየቁኝ፡፡ ፍሎሬንስና ቤተሰቧ ገዳዮቹ ቆራርጠው እስከሚገድሏቸው ተራቸውን እየጠበቁ በቤተክርስቲያን የተቀመጡችበትን ታሪክ እያስታወስኩ ፊቷ ላይ ያለውን የገጀራ ጠባሳ አየሁት፡፡ ያበጠው ይፈንዳ እንጂ እኔማ ቆሜ የምታረድበትን ተራ አልጠባበቅም፡፡
‹‹እንሂድ›› አልኩ፡፡ ‹‹ወደ ሩአግ ምሽግ በእግራችን እንሄዳለን - ወታደሮቻቸው ቅርብ ናቸው፡፡››
ገዳዮቹ ሩአግ ስል ሲሰሙኝ ጊዜ ተናደዱ፡፡
መንቀሳቀስ ብንጀምርም ብዙም መሄድ አልቻልንም፡፡ መንገዱን የድንጋይና የሰው አስከሬን በጣም ስለሞላው የአሎይዜን የመቀመጫ ተሸከርካሪ መግፋቱ አስቸገረን - አንዱ ጎማው በተቀረቀረ ቁጥር ሁላችንም እንቆማን፡፡ የአሎይዜ ልጆችም እያለቀሱ የእናታቸውን ክርኖች ያዙ፡፡
ጓደኞቼን ዢን ፖልንና ካሬጋን ከቡድኑ ነጥዬ ወሰድኳቸው፡፡ ‹‹እናንተ ሁለታችሁ ከኔ ጋር ኑ - ሌሎቻችሁ ከአሎይዜ ጋር ትቆያላችሁ… እና ደግሞ ጸልዩ፡፡ ቱትሲ ወታደሮቹን ፈልጌያቸው እመጣለሁ፡፡ ከዚህ ስፍራ አትሂዱ፤ ያለዚያ በዚህ የሁቱ ጎርፍ መካከል ላገኛችሁ አልችልም፡፡›› አሎይዜ በጥርጣሬ እያየችኝ ‹‹እውነት መሄድሽ ነው? በእርግጠኝት ይገድሉሻል! ይልቅ ወንዶቹ ቢሄዱ ይሻላል›› ስትል ለመነችኝ፡፡
‹‹አይሆንም እኔ ነኝ የምሄደው … እናንተ ብቻ በጸሎታችሁ ላይ አተኩሩ፡፡›› ያን ካልኩ በኋላ ፈረንሳውያኑ ትተውን ከመሄዳቸው በፊት ይዘውን ይሄዱ የነበረበትን አቅጣጫ ተከተልኩ፡፡ ስንሄድ ከአምላክ ጋር በሙሉ ልቤና ነፍሴ እያወራሁ በመቁጠሪያው ጸሎት አደርስ ጀመር፡፡ ‹‹እግዚአብሔር ሆይ! እውነት በሞት ፈፋ ውስጥ እየሄድኩ ነው - እባክህ ድረስልኝ፡፡ በፍቅርህ ኃይል ከልለኝ፡፡ ይህን የምሄድበትን መንገድ ፈጥረኸዋል፤ ስለዚህ እባክህ እነዚህን ገዳዮች የልጅህን ደም እላዩ እንዲያፈሱት አታድርጋቸው፡፡››
ከትልቁ ቡድን ተነጥለን ስንሄድ ሦስት ኢንተርሃምዌዎች ተከተሉን፤ አንዱ እንዲያውም እኔን ዐወቀኝ፡፡ ‹‹ይህችን በረሮ አውቃታለሁ›› አለ፡፡ ‹‹የሊኦናርድ ልጅ እኮ ነች - ለወራት ስንፈልጋት ቆይተናል! አስካሁን አለች ብዬ አላምንም… ሌሎቹን ገድለናቸዋል፤ ግን ይቺ ደቃቃ በረሮ አምልጣናለች!››
በቻልኩት መጠን ፈጥኜ እየተራመድኩና የአባቴን መቁጠሪያ በእጄ አጥብቄ ይዤ ‹‹ጌታ ሆይ›› ስል ጸለይኩ፡፡ ‹‹አንተ ታድነኛለህ፡፡ ፈጣሪዬ እንደምትንከባከበኝ ቃል ገብተህልኛል፣ እንግዲህ አለኝታነትህን አሁኑኑ እፈልጋለሁ፡፡ በጀርባዬ ሰይጣኖችና የሎሶች አሰፍስፈዋል፡፡ አምላክ … እባክህ ጠብቀኝ፡፡ ከነዚህ ሰዎች ልብ ውስጥ ሰይጣኑን አስወጣው፤ ጥላቻቸውንም በቅዱስ ፍቅርህ አሳውረው፡፡›› ድንጋይ ወይንም አስከሬን እንዳያደናቅፈኝ ሳልጠነቀቅ፣ እምነቴን በጌታዬ ላይ ጥዬና ደኅና ወደምሆንበት ስፍራ እንዲመራኝ እግሮቼን እንኳን ማየቴን ትቼ ተራመድኩ፡፡ የምንጓዘው በጣም በፍጥነት ነው፤ ቢሆንም ግን ገዳዮቹ ገጀራዎቻቸውን በአየር ላይ እያወናጨፉ ከበውናል፡፡ ማንም ከለላ የሚሆነን የለም፡፡ ታዲያ ለማጥቃት ምንድነው የሚጠብቁት?
‹‹ከገደሉኝ፣ እግዚአብሔር፣ እንድትምራቸው እለምንሃለሁ፡፡ ልባቸው በጥላቻ ታውሯል፤ ለምን ሊጎዱኝ እንደሚፈልጉም አያውቁትም፡፡››
ግማሽ ኪሎሜትር በዚያን ዓይነት ሁኔታ ከሄድን በኋላ ዢን ፖል ‹‹እዪ ሄደዋል…ሄደዋል!›› አለኝ፡፡
ተመልሼ ሳይ እውነት ኖሯል - ገዳዮቹ ትተውን ተመልሰዋል፡፡ ዢን ፖል በኋላ ላይ ምናልባት የሩአግ ወታደሮች በቅርብ እንዳሉ ስላወቁ ይሆናል ቢልም ትክከለኛውን ምክንያት ግን አውቄዋለሁ፤ በዚያ መንገድ ላይ ሕይወታችን ስላተረፈልን እግዚአብሔርን ማመስገኔን አላቆምኩም!
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ በአንድ የሩአግ ኬላ ብዙ ደርዘኖች ረጃጅም፣ ቀጫችንና ኮስታራ የቱትሲ ወታደሮችን ዘበኝነት ቆመው አየን፡፡ በለየለት ሩጫ ሄጄ እፊት ለፊታቸው ተንበረከክሁ፡፡ ዓይኖቼን ጨፍኜ የምስጋና መዝሙር ዘመርኩላቸው፡፡
‹‹ተመስገን አምላኬ፣ ተመስገን ጌታዬ፣ ድነናል! ተመስገን አምላኬ፣ ደረሳችሁልና፡፡ ተባረኩ፤ ሁላችሁም ተባረኩ! አይ፣ ያለፍንበትን ብታዩልን፡፡ እናመሰግናለን ለ - ››
አስደንጋጭ ቀጭ ቀጭ የሚል የጠመንጃ መሳቢያ ሲሸለቀቅ የሚያሰማው ድምፅ ስላቋረጠኝ የጀመርኩትን ንግግር ለመጨረስ አልቻልኩም፡፡ ዓይኖቼን ገልጬ ሳይ የጠመንጃው አፈሙዝ ፊቴ ላይ ተደግኗል፡፡
ወይ አምላኬ፣ ይህን የቅዠት ሕይወት ይበቃል የምትለው መቼ ይሆን?
ወደ ጠመንጃው አፈሙዝ ቀና ብዬ ካየሁ በኋላ ክፋት ወደሚነበብባቸውና ወደ ቁጡዎቹ የቱትሲው ወታደር ዓይኖች አማተርኩ፡፡ ሃያ ከማይሞሉ ደቂቃዎች በፊት ያፈጠጥኩባቸውን የገዳዩን ዓይኖች አስታወሱኝ፡፡
የዘር ፍጅቱ ከጀመረ ጊዜ ጀምሮ ከመአት ይሰውሩናል ብለን ተስፋ ስናደርግባቸው የቆየነው የሩአግ ወታደሮች እነዚህ ከሆኑ አሁን ለኔ ትክክለኛው የመሞቻ ሰዓቴ ነው፡፡ ጎረቤቶቼ ከድተውኛል፣ ገዳዮቹ እንደዚያ ሲፈልጉኝ ከርመዋል፣ ፈረንሳውያኑ ትተውኛል፣ አሁን ደግሞ ቱትሲ ወገኖቼ ጭንቅላቴን ሊያፈርሱት ቃጥቷቸዋል፡፡
ያንተው ድርሻ ነው፣ እግዚአብሔር፣ ስል በውስጤ ጸለይኩ፡፡ ያንተን ፍቃድ እየፈጸምኩ እስከሆነ ድረስ ኖርኩም ሞትኩ ለኔ ምንም ችግር የለውም፡፡ እዚህ አምጥተኸኛል - መወሰኑ እንግዲህ ያንተው ድርሻ ነው፡፡
ዓይኖቼን አልጨፈንኳቸውም … እናም ያንድ ሰው ዕድሜ ለመሰለኝ ያህል ጊዜ ተፋጠጥን፡፡ በመጨረሻም ገዳዩ ሳፈጥበት እይታውን ወደ ሌላ አቅጣጫ አዞረ፡፡ ሰይጣን ሰውነቱን ትቶት እንደሄደ ሁሉ ጀርባውን አዙሮ ገጀራውን አሽቀንጥሮ ጣለው፡፡ በአንጻሩ ሌሎች ብዙ ዲያብሎሶች የእርሱን ስፍራ ለመተካት ተዘጋጅተዋል፡፡ ቢያንስ 15 ኢንተርሃምዌዎች ከተሸከርካሪው የተወሰኑ እርምጃዎች ርቀት ላይ ገጀራ ይዘው ፊታቸውን ተኮሳትረው ቆመዋል፤ እየተከሰተ ያለውን ነገር ምንነት በማጤን ከጓደኞቼ አንዳቸው እንኳን ለመውረድ አለመድፈራቸውን ያዩ ይዘዋል፡፡ ከመውጣት ውጪ ምንም አማራጭ የለንም፡፡ ሰላሳችንም እዚያ ገዳዮቹን ተጋፍጠን እስክንቆም ድረስ ጓደኞቼ አንድ በአንድ እየዘለሉ ወረዱ፡፡ ሁሉም ወርዶ እንዳለቀ ሁለት የፈረንሳይ ወታደሮች አሎይዜን አወረዷት፤ ልጆቿንም ኬንዛንና ሳሚን ከጎኗ አደረጉላት፡፡ ወታደሮቹ ተሳፈሩና ተሽከርካሪው በአቧራና እርግጠኝነት እጦት ደመና ውስጥ ትቶን በከፍተኛ ፍጥነት ነጎደ፡፡
አንደኛው ገዳይ ‹‹እነዚህን ሁሉ ቱትሲዎች እዩዋቸው›› ሲል በመገረም ተናገረ፡፡ ‹‹እንዴት ነው እስካሁን በሕይወት ሊኖሩ የቻሉት?››
‹‹የፈረንሳይ ወታደሮች ከለላ ሰጥተዋቸው የነበሩት በረሮዎች ናቸው›› አለ ሌላኛው፡፡ ‹‹እስኪ አሁን ማነው የሚያድናችሁ? በረሮ ሁላ!››
ጓደኞቼ በጣም ስለፈሩ መንቀሳቀስ እንኳን ተሳናቸው፡፡ ለጨካኝ ገዳዮች መላ በመዘየድ ባለሙያ የሆንኩ ይመስል ጎሰም አድርገው ምን ማድረግ እንደሚገባን ጠየቁኝ፡፡ ፍሎሬንስና ቤተሰቧ ገዳዮቹ ቆራርጠው እስከሚገድሏቸው ተራቸውን እየጠበቁ በቤተክርስቲያን የተቀመጡችበትን ታሪክ እያስታወስኩ ፊቷ ላይ ያለውን የገጀራ ጠባሳ አየሁት፡፡ ያበጠው ይፈንዳ እንጂ እኔማ ቆሜ የምታረድበትን ተራ አልጠባበቅም፡፡
‹‹እንሂድ›› አልኩ፡፡ ‹‹ወደ ሩአግ ምሽግ በእግራችን እንሄዳለን - ወታደሮቻቸው ቅርብ ናቸው፡፡››
ገዳዮቹ ሩአግ ስል ሲሰሙኝ ጊዜ ተናደዱ፡፡
መንቀሳቀስ ብንጀምርም ብዙም መሄድ አልቻልንም፡፡ መንገዱን የድንጋይና የሰው አስከሬን በጣም ስለሞላው የአሎይዜን የመቀመጫ ተሸከርካሪ መግፋቱ አስቸገረን - አንዱ ጎማው በተቀረቀረ ቁጥር ሁላችንም እንቆማን፡፡ የአሎይዜ ልጆችም እያለቀሱ የእናታቸውን ክርኖች ያዙ፡፡
ጓደኞቼን ዢን ፖልንና ካሬጋን ከቡድኑ ነጥዬ ወሰድኳቸው፡፡ ‹‹እናንተ ሁለታችሁ ከኔ ጋር ኑ - ሌሎቻችሁ ከአሎይዜ ጋር ትቆያላችሁ… እና ደግሞ ጸልዩ፡፡ ቱትሲ ወታደሮቹን ፈልጌያቸው እመጣለሁ፡፡ ከዚህ ስፍራ አትሂዱ፤ ያለዚያ በዚህ የሁቱ ጎርፍ መካከል ላገኛችሁ አልችልም፡፡›› አሎይዜ በጥርጣሬ እያየችኝ ‹‹እውነት መሄድሽ ነው? በእርግጠኝት ይገድሉሻል! ይልቅ ወንዶቹ ቢሄዱ ይሻላል›› ስትል ለመነችኝ፡፡
‹‹አይሆንም እኔ ነኝ የምሄደው … እናንተ ብቻ በጸሎታችሁ ላይ አተኩሩ፡፡›› ያን ካልኩ በኋላ ፈረንሳውያኑ ትተውን ከመሄዳቸው በፊት ይዘውን ይሄዱ የነበረበትን አቅጣጫ ተከተልኩ፡፡ ስንሄድ ከአምላክ ጋር በሙሉ ልቤና ነፍሴ እያወራሁ በመቁጠሪያው ጸሎት አደርስ ጀመር፡፡ ‹‹እግዚአብሔር ሆይ! እውነት በሞት ፈፋ ውስጥ እየሄድኩ ነው - እባክህ ድረስልኝ፡፡ በፍቅርህ ኃይል ከልለኝ፡፡ ይህን የምሄድበትን መንገድ ፈጥረኸዋል፤ ስለዚህ እባክህ እነዚህን ገዳዮች የልጅህን ደም እላዩ እንዲያፈሱት አታድርጋቸው፡፡››
ከትልቁ ቡድን ተነጥለን ስንሄድ ሦስት ኢንተርሃምዌዎች ተከተሉን፤ አንዱ እንዲያውም እኔን ዐወቀኝ፡፡ ‹‹ይህችን በረሮ አውቃታለሁ›› አለ፡፡ ‹‹የሊኦናርድ ልጅ እኮ ነች - ለወራት ስንፈልጋት ቆይተናል! አስካሁን አለች ብዬ አላምንም… ሌሎቹን ገድለናቸዋል፤ ግን ይቺ ደቃቃ በረሮ አምልጣናለች!››
በቻልኩት መጠን ፈጥኜ እየተራመድኩና የአባቴን መቁጠሪያ በእጄ አጥብቄ ይዤ ‹‹ጌታ ሆይ›› ስል ጸለይኩ፡፡ ‹‹አንተ ታድነኛለህ፡፡ ፈጣሪዬ እንደምትንከባከበኝ ቃል ገብተህልኛል፣ እንግዲህ አለኝታነትህን አሁኑኑ እፈልጋለሁ፡፡ በጀርባዬ ሰይጣኖችና የሎሶች አሰፍስፈዋል፡፡ አምላክ … እባክህ ጠብቀኝ፡፡ ከነዚህ ሰዎች ልብ ውስጥ ሰይጣኑን አስወጣው፤ ጥላቻቸውንም በቅዱስ ፍቅርህ አሳውረው፡፡›› ድንጋይ ወይንም አስከሬን እንዳያደናቅፈኝ ሳልጠነቀቅ፣ እምነቴን በጌታዬ ላይ ጥዬና ደኅና ወደምሆንበት ስፍራ እንዲመራኝ እግሮቼን እንኳን ማየቴን ትቼ ተራመድኩ፡፡ የምንጓዘው በጣም በፍጥነት ነው፤ ቢሆንም ግን ገዳዮቹ ገጀራዎቻቸውን በአየር ላይ እያወናጨፉ ከበውናል፡፡ ማንም ከለላ የሚሆነን የለም፡፡ ታዲያ ለማጥቃት ምንድነው የሚጠብቁት?
‹‹ከገደሉኝ፣ እግዚአብሔር፣ እንድትምራቸው እለምንሃለሁ፡፡ ልባቸው በጥላቻ ታውሯል፤ ለምን ሊጎዱኝ እንደሚፈልጉም አያውቁትም፡፡››
ግማሽ ኪሎሜትር በዚያን ዓይነት ሁኔታ ከሄድን በኋላ ዢን ፖል ‹‹እዪ ሄደዋል…ሄደዋል!›› አለኝ፡፡
ተመልሼ ሳይ እውነት ኖሯል - ገዳዮቹ ትተውን ተመልሰዋል፡፡ ዢን ፖል በኋላ ላይ ምናልባት የሩአግ ወታደሮች በቅርብ እንዳሉ ስላወቁ ይሆናል ቢልም ትክከለኛውን ምክንያት ግን አውቄዋለሁ፤ በዚያ መንገድ ላይ ሕይወታችን ስላተረፈልን እግዚአብሔርን ማመስገኔን አላቆምኩም!
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ በአንድ የሩአግ ኬላ ብዙ ደርዘኖች ረጃጅም፣ ቀጫችንና ኮስታራ የቱትሲ ወታደሮችን ዘበኝነት ቆመው አየን፡፡ በለየለት ሩጫ ሄጄ እፊት ለፊታቸው ተንበረከክሁ፡፡ ዓይኖቼን ጨፍኜ የምስጋና መዝሙር ዘመርኩላቸው፡፡
‹‹ተመስገን አምላኬ፣ ተመስገን ጌታዬ፣ ድነናል! ተመስገን አምላኬ፣ ደረሳችሁልና፡፡ ተባረኩ፤ ሁላችሁም ተባረኩ! አይ፣ ያለፍንበትን ብታዩልን፡፡ እናመሰግናለን ለ - ››
አስደንጋጭ ቀጭ ቀጭ የሚል የጠመንጃ መሳቢያ ሲሸለቀቅ የሚያሰማው ድምፅ ስላቋረጠኝ የጀመርኩትን ንግግር ለመጨረስ አልቻልኩም፡፡ ዓይኖቼን ገልጬ ሳይ የጠመንጃው አፈሙዝ ፊቴ ላይ ተደግኗል፡፡
ወይ አምላኬ፣ ይህን የቅዠት ሕይወት ይበቃል የምትለው መቼ ይሆን?
ወደ ጠመንጃው አፈሙዝ ቀና ብዬ ካየሁ በኋላ ክፋት ወደሚነበብባቸውና ወደ ቁጡዎቹ የቱትሲው ወታደር ዓይኖች አማተርኩ፡፡ ሃያ ከማይሞሉ ደቂቃዎች በፊት ያፈጠጥኩባቸውን የገዳዩን ዓይኖች አስታወሱኝ፡፡
የዘር ፍጅቱ ከጀመረ ጊዜ ጀምሮ ከመአት ይሰውሩናል ብለን ተስፋ ስናደርግባቸው የቆየነው የሩአግ ወታደሮች እነዚህ ከሆኑ አሁን ለኔ ትክክለኛው የመሞቻ ሰዓቴ ነው፡፡ ጎረቤቶቼ ከድተውኛል፣ ገዳዮቹ እንደዚያ ሲፈልጉኝ ከርመዋል፣ ፈረንሳውያኑ ትተውኛል፣ አሁን ደግሞ ቱትሲ ወገኖቼ ጭንቅላቴን ሊያፈርሱት ቃጥቷቸዋል፡፡
ያንተው ድርሻ ነው፣ እግዚአብሔር፣ ስል በውስጤ ጸለይኩ፡፡ ያንተን ፍቃድ እየፈጸምኩ እስከሆነ ድረስ ኖርኩም ሞትኩ ለኔ ምንም ችግር የለውም፡፡ እዚህ አምጥተኸኛል - መወሰኑ እንግዲህ ያንተው ድርሻ ነው፡፡
👍2
ቀስ ብዬ እጆቼን በአየር ላይ እያነሳሁ ሁለቱ ጓደኞቼና እኔ ቱትሲዎች መሆናችንን እያብራራሁ ለመቆም ሞከርኩ ‹‹ፈረንሳውያኑ ወታደሮች መንገድ ላይ ጥለውን ሄዱ … የጭፍጨፋው ሌሎች ተራፊዎች ከኋላችን በገዳዮች ተከበዋል፡፡ እባካችሁ እጅግ ከመዘግየቱ በፊት ልትረዷቸው ይገባል፤ ኧረ ድረሱላቸው፡፡››
‹‹አፍሽን ዝጊና መሬቱ ላይ ቁጭ በይ!›› ወታደሩ በጠመንጃው እየጎሰመኝ ጮኸ፡፡
‹‹ቱትሲዎች ከሆናችሁ እንዴት ነው እስካሁን ልትኖሩ የቻላችሁት?!›› ሌላው ጠመንጃውን በኔ ላይ ደግኖ ጮኸ፡፡ ‹‹ሁሉም ሞቷል፣ ሁሉም! እናንተ ራሳችሁ ገዳዮች ናችሁ… የሁቱ ሰላይ ሁላ! ጆሮ ጠቢዎችን ምን እንደምናደርግ ታውቃላችሁ? አርፋችሁ ተቀመጡ፤ እንዳትንቀሳቀሱ - አንዲትም ቃል እንዳትተነፍሱ፤ ዋ ቀስቀስ ትሉና! እያንዳንድሽ ቱትሲ ነኝ፣ ጂኒ ጃንካ ብትዪ የሚሰማሽ ያለ አይምሰልሽ!››በቁጡ ወታደሮች ስለተከበብን ማውራት ፍሬ አልነበረውም፡፡ አፌን ዘግቼ ዕጣ ፈንታዬ ያስቀመጠልኝን እጠብቅ ገባሁ፤ ደቂቃዎች አለፉ፡፡ በቃሌ ጸንቼ ወታደሮቹን እንዲያድኗቸው እንድልክላቸው የሚጠብቁትን አሎይዜንና ሌሎቹን በገዳዮቹ የተከበቡትን አሰብኳቸው፡፡ እንግዲህ እግዜር ይሁናቸዋ፤ ሌላ ምን እላለሁ?
በኋላ ላይ የአማጽያኑ ወታደሮች አዛዥ ሊመረምረን መጣ፡፡ ይጠብቁን የነበሩት ወታደሮች ሰላምታ ሰጡት፤ ‹‹ሻለቃ›› እያሉም ይጠሩታል፡፡ ረጅም፣ እንደዱላ የቀጠነና በሕይወቴ ካየኋቸው ሰዎች ሁሉ የተረጋጋ የሚመስል ነው፡፡ ቤቱን ሰብረን ስንገባ የተያዝን ሌቦች እንደሆንን ሁሉ ገረመመን … የፈረንሳይ ወታደሮች የኢንተርሃምዌውን ሰላይ እንደያዙ በፊታቸው ላይ ይታይ የነበረው ዓይነት ገጽታ ይታይበታል፡፡ ያ ሰው ምን ዕጣ እንደገጠመው አስታውሼ አማተብኩ፡፡ ሻለቃው ከዘር ፍጅቱ የተረፍን መሆናችንን አለማመኑ ያስታውቃል፡፡ ይህንንም በማየቴ በመንገድ ዳር ስለተውናቸው ምስኪን ነፍሶች እጸልይ ጀመር፡፡
በዚች ቅጽበት እግዚአብሔር ለእኛ በድጋሚ ጣልቃ ገባልን፡፡
‹‹ኢማኪዩሌ? ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ?›› ከሻለቃው ጎን የተቀመጠ ወታደር ስሜን እየጠራ ባለማመን አፈጠጠብኝ፡፡ ‹‹ኢማኪዩሌ! አይ፣ አንቺማ አትሆኚም፣ እንዲያው ትሆኚ ይሆን ? አንቺ ነሽ?››
‹‹ባዚል?››
‹‹አንቺ ነሽ!›› ጠመንጃውን አስቀመጠና ተንበርክኮ አቀፈኝ፡፡ ባዚል ቱትሲ አማጽያኑን ደግፎ ለመዋጋት የዘመተ ሁቱ ጎረቤታችን ነው፡፡ ከትምህርት ቤት ጀምሮ እንተዋወቃለን፡፡ እናቴ ለረጅም ዓመታት ተሰጥኦ የነበረውና ጎበዝ ተማሪዋ ስለነበር ትወደዋለች፡፡ እማማ ለእርሱ የተለየ ፍቅር ስለነበራት እቤት ብዙ ጊዜ ስለምትጋብዘው ‹‹የመምህርት ብርቅዬ የቤት እንስሳ›› እንለዋለን፡፡
‹‹ይቺን ልጅ ታውቃታለህ?›› ሻለቃው ባዚል አቅፎኝ ሲጨርስ ጠየቀው፡፡
‹‹እንዴ አዎን አብረን ነው የተማርነው፡፡ ወላጆቿ በመንደራችን እጅግ የተከበሩ ቱትሲዎች ነበሩ - በጣም ጥሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ምንም ችግር የለባትም ሻለቃ … ሰላይነቱ አይነካካትም፡፡ ኢማኪዩሌ የምትለው ሁሉ ፍጹም ሃቅ ነው፡፡›› ባዚልን በምፈልግበት አፍታ ስለላከልኝ አምላኬን በቶሎ አመሰገንኩት፡፡ ወታደሮቹ የደገኗቸውን ጠመንጃዎች ዝቅ አደረጉ፤ ሻለቃውም እጃቸውን ዘርግተው ሰላምታ አቀረቡልኝ፡፡ ‹‹ሻለቃ ንትዋሊ እባላለሁ›› አሉኝ፡፡ ‹‹ስለ ግርታው ይቅርታ፤ በእርግጥ ሰላዮችም በየስፍራው አሉ፡፡ እዚህ አካባቢ አሁንም በጣም አስቸጋሪ ነው፤ ግን ከኛ ጋር ከሆናችሁ ዘንዳ ሐሳብ አይግባችሁ፡፡ ለእናንተ ጦርነቱ አልቆላችኋል … ከአሁኗ ደቂቃ ጀምሮ ከማናቸውም ጥቃት እንከላከላችኋለን፡፡››
‹‹አመሰግናለሁ ሻለቃ፤ እጅጉን የእርስዎን ከለላ የሚፈልጉት ግን ጓደኞቼ ናቸው›› ስል ወዲያውኑ ነገርኳቸው፡፡ ‹‹ፈረንሳውያኑ ወታደሮች የተዉን በኢንተርሃምዌዎቹ መሐል ነው፤ በመሆኑም በመንገዱ ወደ ግማሽ ኪሎሜትር ወርዶ 30 የቱትሲ ርዝራዦች በገዳዮች ተከበው ይገኛሉ፡፡ እስካሁን ድረስ በሕይወት መኖራቸውንም አላውቅም፡፡ እባክዎን …››
ተናግሬ እንኳን ሳልጨርስ ሻለቃው የተወሰኑት ወታደሮች አሎይዜንና ሌሎቹን እንዲያመጧቸው ለአንዱ ምልክት ሰጡት፡፡ ‹‹ስለጓደኞችሽ አትጨነቂ፡፡ እንደርስላቸዋለን፡፡››
‹‹አመሰግናለሁ… ፈጣሪ ይባርክዎ! አዬ፣ ሌላ ምን እላለሁ!›› ወታደሮቹ ሌሎቹን ለማገዝ ሲሄዱ ባዚል ከጎኔ ተቀምጦ በሥጋት የጥያቄ መአት አወረደብኝ - ‹‹ይኸው እቤት ከሄድኩ ስንት ወሬ … የሰፈራችንን ወሬ ሰምተሻል? መምህርት እንዴት ናቸው - እናትሽን ማለቴ ነው? አልበረቱም? ስለ ወላጆቼ፣ ወንድሞቼና እህቶቼስ የሰማሽው ነገር አለ? ለመጨረሻ ጊዜ በጠየቅኋቸው ጊዜ አገሪቱን ለቀው ሊሄዱ እየተዘገጃጁ ነበር… ወጡ እንዴ?››
እጄን በባዚል ክርኖች ላይ ጣል አደረግሁ፡፡ ልቀሰቅስበት የምችለው ሕመም ይታወቀኛል፤ ስለሆነም በተቻለኝ መጠን ረገብ ለማለት ሞከርኩና ‹‹ስለዚህ ጉዳይ እንዴት እንደምነግርህ አላውቅም፣ ባዚል፣ እውነቱን ከመናገር በቀር፡፡ ሁሉም ሞተዋል - የኔም፣ ያንተም ቤተሰብ … በመንደራችን ያለ ቱትሲና ለዘብተኛ ሁቱ ሁሉም ማለት በሚቻል ሁኔታ በሞት ጎዳና ተከታትለው ሄደዋል - አዬ! ደመ-ከልብ ሆነው ቀርተዋል ወንድሜ›› ብዬ አረዳሁት፡፡
መናገር እንደረሳ ሁሉ ብቻ ዝም ብሎ ያስተውለኛል፤ ከዚያም በእግሮቼ ስር ጥቅልል ብሎ ደረቱ ትር ትር እያለ በጠመንጃው ሰደፍ ላይ ያነባ ጀመር፡፡ ምስኪን ባዚል… ወላጆቹን፣ አራት ወንድሞቹንና ሦስት እህቶቹን አጣ፡፡ ውይ አንጀት ሲበላ!
እንደደረስን በዚያን ዓይነት ጥርጣሬ ለምን እንዳስተናገዱን አሁን ገባኝ፡፡ ከእነዚህ ወታደሮች አብዛኞቹ ከዩጋንዳ ድረስ እየተዋጉ ስለመጡ በመንገዳቸው ስለቤተሰቦቻቸው ምንም ወሬ አልሰሙም፡፡ አሁን ሲመለሱ ቤተሰቦቻቸውን በሕይወታቸው ሙሉ ባመኗቸው ሰዎች፣ በጎረቤቶቻቸው፣ ታርደው ያገኟቸዋል፡፡ በአማጽያኑ ምሽግ ቁዘማ ነግሷል፡፡
እኔም ብዙም ደስታ አልተሰማኝም፡፡ ባዚልን በማርዳቴ ተጸጽቻለሁ፤ ደቂቃዎችም ባለፉ ቁጥር አሎይዜንና ቡድኗን የሚፈራው ነገር ገጥሟቸው እንዳይሆን በመስጋት ስለደህንነታቸው በጣም እየጸለይኩ ሳለ የደስተኛዋን ጓደኛዬን የተለመደ ሣቅ እየመጣ ካለው የሩአግ ተሽከርካሪ ሰማሁት፡፡
‹‹ኢማኪዩሌ፣ ይህ የምትጸልዪው ጸሎት ምንም ዓይነት ይሁን ምን መጸለይሽን እንዳትተዪ›› ስትል አሎይዜ እየሳቀች ነገረችኝ፡፡ ‹‹እነዚያ ገዳዮች እኮ ሊቆራርጡን ቢፈልጉም መንቀሳቀስ እንደተሳናቸው ነው እይታቸው የሚያሳየው … እዚያው ባሉበት እንደ በረዶ እኮ ነው የሆኑት! በአንበሶች ጉድጓድ እንደተጣለው እንደ ዳንኤል ነበር እኮ የሆንነው … በአንበሶች ጋጣ እንደተጣለው ዳንኤል ልጄ!›› አሎይዜ ልጆቿን ሳብ አደረገችና ጠበቅ አድርጋ አቀፈቻቸው፤ ከዚያም እንባ በጉንጮቿ እስኪወርድ ድረስ በሣቅ ትንከተከት ገባች፡፡ ልቤ ተነሣሳችና ‹‹አምላክ ከእንግዲህ ከገዳዮቹ ጋር ድጋሚ አያገጣጥመንም፡፡ ይህችን ደፍሮ ለማለት ያደርሰኝ እንደሆነ ካሁን በፊት አላውቅም ነበር፤ ለማንኛውም አሁን ጭፍጨፋው አብቅቷል - እግዚአብሔር አትርፎ አዲስ ሕይወት ሰጥቶናል፡፡ አምላክ ይመስገን! እናመሰግንሃለን ፈጣሪ!›› አልኩ፡፡
አሎይዜ ሣቅ ብላ ‹‹ይሁን ይደረግልን፣ ኢማኪዩሌ… ይሁና!›› አለችኝ፡፡
የአሎይዜ ሳቂታነትና ነጻነት ያለበት መንፈሷ ያዘኑትን
‹‹አፍሽን ዝጊና መሬቱ ላይ ቁጭ በይ!›› ወታደሩ በጠመንጃው እየጎሰመኝ ጮኸ፡፡
‹‹ቱትሲዎች ከሆናችሁ እንዴት ነው እስካሁን ልትኖሩ የቻላችሁት?!›› ሌላው ጠመንጃውን በኔ ላይ ደግኖ ጮኸ፡፡ ‹‹ሁሉም ሞቷል፣ ሁሉም! እናንተ ራሳችሁ ገዳዮች ናችሁ… የሁቱ ሰላይ ሁላ! ጆሮ ጠቢዎችን ምን እንደምናደርግ ታውቃላችሁ? አርፋችሁ ተቀመጡ፤ እንዳትንቀሳቀሱ - አንዲትም ቃል እንዳትተነፍሱ፤ ዋ ቀስቀስ ትሉና! እያንዳንድሽ ቱትሲ ነኝ፣ ጂኒ ጃንካ ብትዪ የሚሰማሽ ያለ አይምሰልሽ!››በቁጡ ወታደሮች ስለተከበብን ማውራት ፍሬ አልነበረውም፡፡ አፌን ዘግቼ ዕጣ ፈንታዬ ያስቀመጠልኝን እጠብቅ ገባሁ፤ ደቂቃዎች አለፉ፡፡ በቃሌ ጸንቼ ወታደሮቹን እንዲያድኗቸው እንድልክላቸው የሚጠብቁትን አሎይዜንና ሌሎቹን በገዳዮቹ የተከበቡትን አሰብኳቸው፡፡ እንግዲህ እግዜር ይሁናቸዋ፤ ሌላ ምን እላለሁ?
በኋላ ላይ የአማጽያኑ ወታደሮች አዛዥ ሊመረምረን መጣ፡፡ ይጠብቁን የነበሩት ወታደሮች ሰላምታ ሰጡት፤ ‹‹ሻለቃ›› እያሉም ይጠሩታል፡፡ ረጅም፣ እንደዱላ የቀጠነና በሕይወቴ ካየኋቸው ሰዎች ሁሉ የተረጋጋ የሚመስል ነው፡፡ ቤቱን ሰብረን ስንገባ የተያዝን ሌቦች እንደሆንን ሁሉ ገረመመን … የፈረንሳይ ወታደሮች የኢንተርሃምዌውን ሰላይ እንደያዙ በፊታቸው ላይ ይታይ የነበረው ዓይነት ገጽታ ይታይበታል፡፡ ያ ሰው ምን ዕጣ እንደገጠመው አስታውሼ አማተብኩ፡፡ ሻለቃው ከዘር ፍጅቱ የተረፍን መሆናችንን አለማመኑ ያስታውቃል፡፡ ይህንንም በማየቴ በመንገድ ዳር ስለተውናቸው ምስኪን ነፍሶች እጸልይ ጀመር፡፡
በዚች ቅጽበት እግዚአብሔር ለእኛ በድጋሚ ጣልቃ ገባልን፡፡
‹‹ኢማኪዩሌ? ኢማኪዩሌ ኢሊባጊዛ?›› ከሻለቃው ጎን የተቀመጠ ወታደር ስሜን እየጠራ ባለማመን አፈጠጠብኝ፡፡ ‹‹ኢማኪዩሌ! አይ፣ አንቺማ አትሆኚም፣ እንዲያው ትሆኚ ይሆን ? አንቺ ነሽ?››
‹‹ባዚል?››
‹‹አንቺ ነሽ!›› ጠመንጃውን አስቀመጠና ተንበርክኮ አቀፈኝ፡፡ ባዚል ቱትሲ አማጽያኑን ደግፎ ለመዋጋት የዘመተ ሁቱ ጎረቤታችን ነው፡፡ ከትምህርት ቤት ጀምሮ እንተዋወቃለን፡፡ እናቴ ለረጅም ዓመታት ተሰጥኦ የነበረውና ጎበዝ ተማሪዋ ስለነበር ትወደዋለች፡፡ እማማ ለእርሱ የተለየ ፍቅር ስለነበራት እቤት ብዙ ጊዜ ስለምትጋብዘው ‹‹የመምህርት ብርቅዬ የቤት እንስሳ›› እንለዋለን፡፡
‹‹ይቺን ልጅ ታውቃታለህ?›› ሻለቃው ባዚል አቅፎኝ ሲጨርስ ጠየቀው፡፡
‹‹እንዴ አዎን አብረን ነው የተማርነው፡፡ ወላጆቿ በመንደራችን እጅግ የተከበሩ ቱትሲዎች ነበሩ - በጣም ጥሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ምንም ችግር የለባትም ሻለቃ … ሰላይነቱ አይነካካትም፡፡ ኢማኪዩሌ የምትለው ሁሉ ፍጹም ሃቅ ነው፡፡›› ባዚልን በምፈልግበት አፍታ ስለላከልኝ አምላኬን በቶሎ አመሰገንኩት፡፡ ወታደሮቹ የደገኗቸውን ጠመንጃዎች ዝቅ አደረጉ፤ ሻለቃውም እጃቸውን ዘርግተው ሰላምታ አቀረቡልኝ፡፡ ‹‹ሻለቃ ንትዋሊ እባላለሁ›› አሉኝ፡፡ ‹‹ስለ ግርታው ይቅርታ፤ በእርግጥ ሰላዮችም በየስፍራው አሉ፡፡ እዚህ አካባቢ አሁንም በጣም አስቸጋሪ ነው፤ ግን ከኛ ጋር ከሆናችሁ ዘንዳ ሐሳብ አይግባችሁ፡፡ ለእናንተ ጦርነቱ አልቆላችኋል … ከአሁኗ ደቂቃ ጀምሮ ከማናቸውም ጥቃት እንከላከላችኋለን፡፡››
‹‹አመሰግናለሁ ሻለቃ፤ እጅጉን የእርስዎን ከለላ የሚፈልጉት ግን ጓደኞቼ ናቸው›› ስል ወዲያውኑ ነገርኳቸው፡፡ ‹‹ፈረንሳውያኑ ወታደሮች የተዉን በኢንተርሃምዌዎቹ መሐል ነው፤ በመሆኑም በመንገዱ ወደ ግማሽ ኪሎሜትር ወርዶ 30 የቱትሲ ርዝራዦች በገዳዮች ተከበው ይገኛሉ፡፡ እስካሁን ድረስ በሕይወት መኖራቸውንም አላውቅም፡፡ እባክዎን …››
ተናግሬ እንኳን ሳልጨርስ ሻለቃው የተወሰኑት ወታደሮች አሎይዜንና ሌሎቹን እንዲያመጧቸው ለአንዱ ምልክት ሰጡት፡፡ ‹‹ስለጓደኞችሽ አትጨነቂ፡፡ እንደርስላቸዋለን፡፡››
‹‹አመሰግናለሁ… ፈጣሪ ይባርክዎ! አዬ፣ ሌላ ምን እላለሁ!›› ወታደሮቹ ሌሎቹን ለማገዝ ሲሄዱ ባዚል ከጎኔ ተቀምጦ በሥጋት የጥያቄ መአት አወረደብኝ - ‹‹ይኸው እቤት ከሄድኩ ስንት ወሬ … የሰፈራችንን ወሬ ሰምተሻል? መምህርት እንዴት ናቸው - እናትሽን ማለቴ ነው? አልበረቱም? ስለ ወላጆቼ፣ ወንድሞቼና እህቶቼስ የሰማሽው ነገር አለ? ለመጨረሻ ጊዜ በጠየቅኋቸው ጊዜ አገሪቱን ለቀው ሊሄዱ እየተዘገጃጁ ነበር… ወጡ እንዴ?››
እጄን በባዚል ክርኖች ላይ ጣል አደረግሁ፡፡ ልቀሰቅስበት የምችለው ሕመም ይታወቀኛል፤ ስለሆነም በተቻለኝ መጠን ረገብ ለማለት ሞከርኩና ‹‹ስለዚህ ጉዳይ እንዴት እንደምነግርህ አላውቅም፣ ባዚል፣ እውነቱን ከመናገር በቀር፡፡ ሁሉም ሞተዋል - የኔም፣ ያንተም ቤተሰብ … በመንደራችን ያለ ቱትሲና ለዘብተኛ ሁቱ ሁሉም ማለት በሚቻል ሁኔታ በሞት ጎዳና ተከታትለው ሄደዋል - አዬ! ደመ-ከልብ ሆነው ቀርተዋል ወንድሜ›› ብዬ አረዳሁት፡፡
መናገር እንደረሳ ሁሉ ብቻ ዝም ብሎ ያስተውለኛል፤ ከዚያም በእግሮቼ ስር ጥቅልል ብሎ ደረቱ ትር ትር እያለ በጠመንጃው ሰደፍ ላይ ያነባ ጀመር፡፡ ምስኪን ባዚል… ወላጆቹን፣ አራት ወንድሞቹንና ሦስት እህቶቹን አጣ፡፡ ውይ አንጀት ሲበላ!
እንደደረስን በዚያን ዓይነት ጥርጣሬ ለምን እንዳስተናገዱን አሁን ገባኝ፡፡ ከእነዚህ ወታደሮች አብዛኞቹ ከዩጋንዳ ድረስ እየተዋጉ ስለመጡ በመንገዳቸው ስለቤተሰቦቻቸው ምንም ወሬ አልሰሙም፡፡ አሁን ሲመለሱ ቤተሰቦቻቸውን በሕይወታቸው ሙሉ ባመኗቸው ሰዎች፣ በጎረቤቶቻቸው፣ ታርደው ያገኟቸዋል፡፡ በአማጽያኑ ምሽግ ቁዘማ ነግሷል፡፡
እኔም ብዙም ደስታ አልተሰማኝም፡፡ ባዚልን በማርዳቴ ተጸጽቻለሁ፤ ደቂቃዎችም ባለፉ ቁጥር አሎይዜንና ቡድኗን የሚፈራው ነገር ገጥሟቸው እንዳይሆን በመስጋት ስለደህንነታቸው በጣም እየጸለይኩ ሳለ የደስተኛዋን ጓደኛዬን የተለመደ ሣቅ እየመጣ ካለው የሩአግ ተሽከርካሪ ሰማሁት፡፡
‹‹ኢማኪዩሌ፣ ይህ የምትጸልዪው ጸሎት ምንም ዓይነት ይሁን ምን መጸለይሽን እንዳትተዪ›› ስትል አሎይዜ እየሳቀች ነገረችኝ፡፡ ‹‹እነዚያ ገዳዮች እኮ ሊቆራርጡን ቢፈልጉም መንቀሳቀስ እንደተሳናቸው ነው እይታቸው የሚያሳየው … እዚያው ባሉበት እንደ በረዶ እኮ ነው የሆኑት! በአንበሶች ጉድጓድ እንደተጣለው እንደ ዳንኤል ነበር እኮ የሆንነው … በአንበሶች ጋጣ እንደተጣለው ዳንኤል ልጄ!›› አሎይዜ ልጆቿን ሳብ አደረገችና ጠበቅ አድርጋ አቀፈቻቸው፤ ከዚያም እንባ በጉንጮቿ እስኪወርድ ድረስ በሣቅ ትንከተከት ገባች፡፡ ልቤ ተነሣሳችና ‹‹አምላክ ከእንግዲህ ከገዳዮቹ ጋር ድጋሚ አያገጣጥመንም፡፡ ይህችን ደፍሮ ለማለት ያደርሰኝ እንደሆነ ካሁን በፊት አላውቅም ነበር፤ ለማንኛውም አሁን ጭፍጨፋው አብቅቷል - እግዚአብሔር አትርፎ አዲስ ሕይወት ሰጥቶናል፡፡ አምላክ ይመስገን! እናመሰግንሃለን ፈጣሪ!›› አልኩ፡፡
አሎይዜ ሣቅ ብላ ‹‹ይሁን ይደረግልን፣ ኢማኪዩሌ… ይሁና!›› አለችኝ፡፡
የአሎይዜ ሳቂታነትና ነጻነት ያለበት መንፈሷ ያዘኑትን
👍1
ወታደሮች አስደሰታቸው፡፡ በምሽቱ ባሳለፍናቸው የመጀመሪያዎቹ ጥቂት ሰዓታት እስካሁን ስላገኘቻቸው ዝነኛ ሰዎች የተለያዩ ነገሮችን በማውጋት ስታዝናናቸው ቆየች ከሁሉም በላይ የተማረኩት ግን በማይናወጠው አዎንታዊ ምኞቷ ነው - በሕይወቷ ስለገጠማት ዕጣ በፍጹም አታማርርም - እያንዳንዷንም ቅጽበት በተቻላት መጠን ትጠቀምባታለች አሎይዜና እኔ በጣም ስለተግባባን ሻለቃ ንዋትሊ እናቴ እንደሆነች ጠየቁኝ፡፡ ‹‹አይደለችም›› ስል መለስኩለት፤ ግን እንደ ልጇ ነው የምታየኝ፡፡ ወላጆቼና ሁለቱ ወንድሞቼ በእርግጥ የጭፍጨፋው ሰለባዎች ናቸው - ሌሎቹም ዘመድ አዝማዶቼ እንዲሁ፡፡
‹‹ይቅርታ›› አሉ ሻለቃው ‹‹ትወቅሱናላችሁ?››
‹‹ምን ማለትዎ ነው?›› ስል ጠየቅኋቸው በጥያቄያቸው ተደናግሬ፡፡
‹‹በተከሰተው ነገር ብዙዎቹ ወታደሮቼ ራሳቸውን ይወቅሳሉ፡፡ የራሳቸውን ቤተሰብ ጨምሮ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ቱትሲዎች ሲገደሉ ኪጋሊን ለመቆጣጠር ስንዋጋ ብዙ ጊዜ እንደፈጀን ያስባሉ፡፡ እዚህ ለመድረስ ረጅም ጊዜ እንደወሰድን ይሰማቸዋል፡፡››
‹‹እንደዚያ ማሰብ የለባቸውም ሻለቃ - የእናንተ ችግር አይደለም፡፡ እኛን ለማዳን ነው እኮ የተዋጋችሁት … ዲያብሎስን ነው የተፋለማችሁት፡፡ አሁን ተመሳሳይ ጦርነት እንዳይመጣብን መጣር አለብን፡፡ መግደልን አቁመን እንዴት ምኅረት ማድረግ እንዳለብን እንማር፡፡››
ባለመስማማት ራሳቸውን ነቀነቁብኝ፡፡ ‹‹ስለ እግዚአብሔር ወይንም ስለ ዲያብሎስ አታውሪልኝ - ይህን ማን እንዳደረገው አውቃለሁ፡፡ ለምትፈልጊያቸው ሁሉ ምኅረት ማድረግ ትችያለሽ፣ ኢማኪዩሌ፡፡ አንቺ ግን ምናልባትም እኔ ያየሁትን ያህል የጅምላ መቃብሮች አላየሽም፡፡ እነዚያን መቃብሮች የሞሉት ሰዎች አሁንም እዚያው ናቸው፤ እና እመኝኝ ገዳዮቹ ምኅረትሽ የሚገባቸው አይደሉም፡፡ መገደል አለባቸው፤ ስለሆነም እኔ የእጃቸውን መስጠትን እመርጣለሁ፡፡ ባይሆን ገድዬ ይቅር እላቸዋለሁ፡፡
ሻለቃው በቅርብ ያለ የባፕቲስት ቤተክርስቲያንን አመለከቱን፡፡ ‹‹ሌሎች ከግድያው የተረፉ ሰዎችን እዚያ ታገኟቸዋላችሁ፡፡ ስለናንተ ምን እንደምናደርግ እስክንወስን ድረስ እዚያው ሁኑ፤ ደግሞ እንዳትዟዟሩ፡፡ አስታውሱ፣ አሁንም ቢሆን በጦርነት ቀጣና ውስጥ ናችሁ፡፡ ጥቂት ኢንተርሃምዌዎች ቢያገኟችሁ እናንተ እንደምትምሯቸው አይምሯችሁም፡፡››
የኔ ቡድን ከሌሎች አንድ መቶ ከሚሆኑ ሌሎች የተረፉ ቱትሲዎች ጋር በቤተክርስቲያኑ ቆየ፡፡ በዚያ ስፍራ አልጋም ሆነ ብርድልብስ የለም፡፡ ከራሳችን በላይ ጣራ በመኖሩ ግን ደስተኞች ነን፡፡ በዚያም ላይ በእግዚአብሔር ቤት መሆናችን አስደስቶናል፡፡ ባዚል ምግብ ስለሰጠን እኔ አዘገጋጅ ጀመር፡፡ ውጪ ላይ እሳት ለማያያዝ ስሞክር አንዳች መጥፎ ሽታ አጥወለወለኝ፡፡
‹‹በፈጣሪ ስም ይህ ሽታ ምንድነው?›› ስል አንደኛውን እኛን እንዲጠብቅ የተመደበውን ወታደር ጠየቅሁት፡፡ እጄን ይዞ ምንም ሳይናገር ወደ ቤተክርስቲያኑ ጓሮ ወሰደኝ፡፡ ከሲዖል የመጣ ምስል ነው ማለት ይቻላል - በመቶዎች የሚቆጠር ሬሳ በሬሳ ላይ እንደ ግንድ ተከምሯል፡፡ ላዩን ደግሞ ጥቁር የዝንብ ምንጣፍ ሸፍኖታል፤ አሞራም ላይ ላዩን ይራኮትበታል፡፡ አንድ ሽማግሌ ሰውዬ በክምሩ ዳርቻ ቆመው ውሾችን በዱላ ያባርራሉ፡፡
አፌን ሸፈንኩ፤ ዓይኖቼም በመሸበር ፈጠጡ፡፡ ከዚያም ወታደሩ ከክምሩ አለፍ ብሎ 30 ሜትር ርዝመትና 20 ሜትር ጥልቀት ያለውን ጉድጓድ አመለከተኝ፡፡ በአሥር ሺዎች በሚቆጠር አስከሬን የተሞላ ነው፡፡ ራሴን አዞርኩ፣ አስመለሰኝና ወደ ቤተክርስቲያኑ ግቢ ፊተኛ ክፍል እየተንገደገድኩ ሄድኩ፡፡ ወታደሩም ምንም ሳይተነፍስ ተከተለኝ፡፡
‹‹የዚህ አካባቢ ሰው ነህ?›› ስል ጠየቅሁት፡፡ ራሱን በአዎንታ ስለነቀነቀልኝ በዚያ እየበሰበሰ ባለ የሰው ክምር ውስጥ አንድ ቦታ ቤተሰቡ እንዳለበት ገባኝ፡፡ ሰቀቀኑ ቃላት ከሚገልጹት በላይ ነው፡፡
ከስንት ዓመት፣ ከስንትስ ትውልድ በኋላ ይሆን ሩዋንዳ ከዚህ አሰቃቂ ድርጊት የምታገግመው? የቆሰሉ አንጀቶቻችንስ በምን ያህል ጊዜ ይሽሩ ይሆን? የደደሩት ልቦቻችን በምን ያክል ጊዜ ይመለሳሉ? ለኔ ረጅም ጊዜ ሆኖ ታየኝ፡፡ የወታደሩን ዓይኖች ሳይ ሩዋንዳን ለቅቄ መሄድ እንዳለብኝ ገባኝ፡፡
ቢያንስ ለተወሰነ ጊዜ የዚህችን ሀገር ሰቆቃና ሥቃይ ትቼ መሄድ አለብኝ፡፡ እግዚአብሔር ሌሎች ጉዳተኞች እንዲድኑ አግዝ ዘንድ ይህን አንዳደርግ እንደፈቀደ ስለማውቅ ጊዜና ቦታ ብቻ የሚፈቅዱልኝን በማመዛዘን የምወስንበት ሁኔታ ያስፈልገኛል፡፡ መጀመሪያ ራሴን ማዳን አለብኝ ሌሎቹን ለማገዝ - በፈረንሳውያን ምሽግ ያሉትን ወላጅ አልባዎች፣ ልባቸው በቀል የተሞላውን ሻለቃ፣ አሁንም መግደል በዓይናቸው ላይ የሚነበብባቸውን አራጆችና ሐዘኑ ነፍሱን ያፈነችበት ከፊት ለፊቴ የቆመው ወታደር - ሁሉንም፡፡
እሄዳለሁ፣ ግን ገና ጊዜ መጠበቅ አለብኝ፡፡ መጀመሪያ ብዙ ማድረግ ይኖርብኛል፤ በተጨማሪም ምንም ሥራ፣ ገንዘብም ሆነ ራእይ የለኝም፡፡ ያለኝ ብቸኛው ነገር የለበስኳቸው ልብሶችና በኪሴ ያለው የአባቴ መቁጠሪያ ነው፡፡ ጓደኞቼና እኔ አብዛኛውን ጊዜያችንን ያለ ምንም ገንዘብ ወደ ኪጋሊ እንዴት መሄድ እንደምንችል በማሰብ ከአማጽያኑ ታጋዮች ጋር ለተወሰኑ ቀናት ቆየን፡፡ አንዴ እዚያ ከደረስን አሥራ ሁለታችንም አሎይዜ ቤት ልንቆይ እንችላለን፣ አሁንም ቢሆን ግን አስቸጋሪውን የአምስት ሰዓት ጉዞ ማድረግ የምንችልበት ምንም መንገድ አልነበረንም፡፡ በግሌ ለቀናት ጸልዬበት ሁሉም አንደኔ እንዲጸልዩ ጠየቅሁ፡፡ በመጨረሻም እግዚአብሔር በምላሹ ሻለቃ ንትዋሊን ከነመፍትሔው ላከልን፡፡ ሻለቃው አሎይዜ በር ላይ የሚያደርሰን የጭነት ተሸከርካሪ ከነዘዋሪው ሰጡን፡፡ ያ ብቻ አይደለም፤ ተሸከርካሪው ላይ ወጥተን ስናበቃ ብዙ ኬሻ ሩዝ፣ ዱቄት፣ ስኳር፣ ባቄላ፣ ቡና፤ የቆርቆሮ ወተትና ዘይት አስጫኑልን፡፡ ለረጅም ጊዜ ካየሁት ምግብ ሁሉ በላይ ሲሆን ለወራት ሊያቆየን ከሚችለውም የበለጠ ነው፡፡ ደኅና ሁኑ በማለት እጆቻችንን ስናውለበልብና ወደ ኪጋሊ ስናመራ ሻለቃውን ለችሮታቸው ደጋግመን አመስግነናቸዋል፡፡
ከተወሰኑ ወራት በፊት ቢሆን ወከባ የበዛበት የሥራ ቀን ይሆን በነበረ ዕለት ቀትር ላይ ከዋና ከተማዋ ደረስን፡፡ ወደ አስፈሪው ከተማ ገባን፡፡ መንገዶቹ አልፎ አልፎ ከሚመጣው የተመድ የጭነት ተሸከርካሪ ወይም መንገድ ውር ውር ከሚሉት ከሩአግ አነስተኛ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች በስተቀር የሚንቀሳቀስ አልነበረባቸውም፡፡ ያሉትም እነዚህ ተሽከርካሪዎች በመንገዶቹ ያሉትን የሰው አስከሬኖች ወይንም ወታደሮቹ እነዚህን አስከሬኖች እንዳይበሉ በጥይት መትተው የገደሏቸውን ዉሾች ላለመዳጥ ተጠንቅቀው ይሄዳሉ፡፡ አየሩ ሞት ሞት ይሸታል፤ ንፋሱም ሰው በሌለባቸው ቤቶች ውስጥ ከሰው ላይ እንደተነሡ መናፍስት ሲሄድ ይሰማኛል፡፡ እጅግ ብዙ ሕንጻዎች በጥይትና በአዳፍኔ ተኩስ ተቃጥለውና ተበሳስተው ፈራርሰው ወድቀዋል፡፡ የሱቆች በሮች ከማጠፊያዎቻቸው ተገነጣጥለዋል፣ የዕቃ መጋዘኖችም ተዘርፈዋል፡፡ አልፎ አልፎም በርቀት ፍንዳታዎች ይሰሙናል፡፡ በአሥራዎቹ ዕድሜዬ ላይ ሆኜ ደማቅ ሰማያዊ መብራቶቿና በሰው የሚጨናነቁት መንገዶቿ ያስደመሙኝን ውቧን ከተማ በዚህ ወቅት ላውቃት አልቻልኩም፡፡
ዘዋሪው ‹‹ተጠንቅቃችሁ ተጓዙ›› ሲል አስጠነቀቀን፡፡ ‹‹በየሄዳችሁበት ፈንጂዎች ተቀብረዋል … የት የት እንደቀበርና
‹‹ይቅርታ›› አሉ ሻለቃው ‹‹ትወቅሱናላችሁ?››
‹‹ምን ማለትዎ ነው?›› ስል ጠየቅኋቸው በጥያቄያቸው ተደናግሬ፡፡
‹‹በተከሰተው ነገር ብዙዎቹ ወታደሮቼ ራሳቸውን ይወቅሳሉ፡፡ የራሳቸውን ቤተሰብ ጨምሮ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ቱትሲዎች ሲገደሉ ኪጋሊን ለመቆጣጠር ስንዋጋ ብዙ ጊዜ እንደፈጀን ያስባሉ፡፡ እዚህ ለመድረስ ረጅም ጊዜ እንደወሰድን ይሰማቸዋል፡፡››
‹‹እንደዚያ ማሰብ የለባቸውም ሻለቃ - የእናንተ ችግር አይደለም፡፡ እኛን ለማዳን ነው እኮ የተዋጋችሁት … ዲያብሎስን ነው የተፋለማችሁት፡፡ አሁን ተመሳሳይ ጦርነት እንዳይመጣብን መጣር አለብን፡፡ መግደልን አቁመን እንዴት ምኅረት ማድረግ እንዳለብን እንማር፡፡››
ባለመስማማት ራሳቸውን ነቀነቁብኝ፡፡ ‹‹ስለ እግዚአብሔር ወይንም ስለ ዲያብሎስ አታውሪልኝ - ይህን ማን እንዳደረገው አውቃለሁ፡፡ ለምትፈልጊያቸው ሁሉ ምኅረት ማድረግ ትችያለሽ፣ ኢማኪዩሌ፡፡ አንቺ ግን ምናልባትም እኔ ያየሁትን ያህል የጅምላ መቃብሮች አላየሽም፡፡ እነዚያን መቃብሮች የሞሉት ሰዎች አሁንም እዚያው ናቸው፤ እና እመኝኝ ገዳዮቹ ምኅረትሽ የሚገባቸው አይደሉም፡፡ መገደል አለባቸው፤ ስለሆነም እኔ የእጃቸውን መስጠትን እመርጣለሁ፡፡ ባይሆን ገድዬ ይቅር እላቸዋለሁ፡፡
ሻለቃው በቅርብ ያለ የባፕቲስት ቤተክርስቲያንን አመለከቱን፡፡ ‹‹ሌሎች ከግድያው የተረፉ ሰዎችን እዚያ ታገኟቸዋላችሁ፡፡ ስለናንተ ምን እንደምናደርግ እስክንወስን ድረስ እዚያው ሁኑ፤ ደግሞ እንዳትዟዟሩ፡፡ አስታውሱ፣ አሁንም ቢሆን በጦርነት ቀጣና ውስጥ ናችሁ፡፡ ጥቂት ኢንተርሃምዌዎች ቢያገኟችሁ እናንተ እንደምትምሯቸው አይምሯችሁም፡፡››
የኔ ቡድን ከሌሎች አንድ መቶ ከሚሆኑ ሌሎች የተረፉ ቱትሲዎች ጋር በቤተክርስቲያኑ ቆየ፡፡ በዚያ ስፍራ አልጋም ሆነ ብርድልብስ የለም፡፡ ከራሳችን በላይ ጣራ በመኖሩ ግን ደስተኞች ነን፡፡ በዚያም ላይ በእግዚአብሔር ቤት መሆናችን አስደስቶናል፡፡ ባዚል ምግብ ስለሰጠን እኔ አዘገጋጅ ጀመር፡፡ ውጪ ላይ እሳት ለማያያዝ ስሞክር አንዳች መጥፎ ሽታ አጥወለወለኝ፡፡
‹‹በፈጣሪ ስም ይህ ሽታ ምንድነው?›› ስል አንደኛውን እኛን እንዲጠብቅ የተመደበውን ወታደር ጠየቅሁት፡፡ እጄን ይዞ ምንም ሳይናገር ወደ ቤተክርስቲያኑ ጓሮ ወሰደኝ፡፡ ከሲዖል የመጣ ምስል ነው ማለት ይቻላል - በመቶዎች የሚቆጠር ሬሳ በሬሳ ላይ እንደ ግንድ ተከምሯል፡፡ ላዩን ደግሞ ጥቁር የዝንብ ምንጣፍ ሸፍኖታል፤ አሞራም ላይ ላዩን ይራኮትበታል፡፡ አንድ ሽማግሌ ሰውዬ በክምሩ ዳርቻ ቆመው ውሾችን በዱላ ያባርራሉ፡፡
አፌን ሸፈንኩ፤ ዓይኖቼም በመሸበር ፈጠጡ፡፡ ከዚያም ወታደሩ ከክምሩ አለፍ ብሎ 30 ሜትር ርዝመትና 20 ሜትር ጥልቀት ያለውን ጉድጓድ አመለከተኝ፡፡ በአሥር ሺዎች በሚቆጠር አስከሬን የተሞላ ነው፡፡ ራሴን አዞርኩ፣ አስመለሰኝና ወደ ቤተክርስቲያኑ ግቢ ፊተኛ ክፍል እየተንገደገድኩ ሄድኩ፡፡ ወታደሩም ምንም ሳይተነፍስ ተከተለኝ፡፡
‹‹የዚህ አካባቢ ሰው ነህ?›› ስል ጠየቅሁት፡፡ ራሱን በአዎንታ ስለነቀነቀልኝ በዚያ እየበሰበሰ ባለ የሰው ክምር ውስጥ አንድ ቦታ ቤተሰቡ እንዳለበት ገባኝ፡፡ ሰቀቀኑ ቃላት ከሚገልጹት በላይ ነው፡፡
ከስንት ዓመት፣ ከስንትስ ትውልድ በኋላ ይሆን ሩዋንዳ ከዚህ አሰቃቂ ድርጊት የምታገግመው? የቆሰሉ አንጀቶቻችንስ በምን ያህል ጊዜ ይሽሩ ይሆን? የደደሩት ልቦቻችን በምን ያክል ጊዜ ይመለሳሉ? ለኔ ረጅም ጊዜ ሆኖ ታየኝ፡፡ የወታደሩን ዓይኖች ሳይ ሩዋንዳን ለቅቄ መሄድ እንዳለብኝ ገባኝ፡፡
ቢያንስ ለተወሰነ ጊዜ የዚህችን ሀገር ሰቆቃና ሥቃይ ትቼ መሄድ አለብኝ፡፡ እግዚአብሔር ሌሎች ጉዳተኞች እንዲድኑ አግዝ ዘንድ ይህን አንዳደርግ እንደፈቀደ ስለማውቅ ጊዜና ቦታ ብቻ የሚፈቅዱልኝን በማመዛዘን የምወስንበት ሁኔታ ያስፈልገኛል፡፡ መጀመሪያ ራሴን ማዳን አለብኝ ሌሎቹን ለማገዝ - በፈረንሳውያን ምሽግ ያሉትን ወላጅ አልባዎች፣ ልባቸው በቀል የተሞላውን ሻለቃ፣ አሁንም መግደል በዓይናቸው ላይ የሚነበብባቸውን አራጆችና ሐዘኑ ነፍሱን ያፈነችበት ከፊት ለፊቴ የቆመው ወታደር - ሁሉንም፡፡
እሄዳለሁ፣ ግን ገና ጊዜ መጠበቅ አለብኝ፡፡ መጀመሪያ ብዙ ማድረግ ይኖርብኛል፤ በተጨማሪም ምንም ሥራ፣ ገንዘብም ሆነ ራእይ የለኝም፡፡ ያለኝ ብቸኛው ነገር የለበስኳቸው ልብሶችና በኪሴ ያለው የአባቴ መቁጠሪያ ነው፡፡ ጓደኞቼና እኔ አብዛኛውን ጊዜያችንን ያለ ምንም ገንዘብ ወደ ኪጋሊ እንዴት መሄድ እንደምንችል በማሰብ ከአማጽያኑ ታጋዮች ጋር ለተወሰኑ ቀናት ቆየን፡፡ አንዴ እዚያ ከደረስን አሥራ ሁለታችንም አሎይዜ ቤት ልንቆይ እንችላለን፣ አሁንም ቢሆን ግን አስቸጋሪውን የአምስት ሰዓት ጉዞ ማድረግ የምንችልበት ምንም መንገድ አልነበረንም፡፡ በግሌ ለቀናት ጸልዬበት ሁሉም አንደኔ እንዲጸልዩ ጠየቅሁ፡፡ በመጨረሻም እግዚአብሔር በምላሹ ሻለቃ ንትዋሊን ከነመፍትሔው ላከልን፡፡ ሻለቃው አሎይዜ በር ላይ የሚያደርሰን የጭነት ተሸከርካሪ ከነዘዋሪው ሰጡን፡፡ ያ ብቻ አይደለም፤ ተሸከርካሪው ላይ ወጥተን ስናበቃ ብዙ ኬሻ ሩዝ፣ ዱቄት፣ ስኳር፣ ባቄላ፣ ቡና፤ የቆርቆሮ ወተትና ዘይት አስጫኑልን፡፡ ለረጅም ጊዜ ካየሁት ምግብ ሁሉ በላይ ሲሆን ለወራት ሊያቆየን ከሚችለውም የበለጠ ነው፡፡ ደኅና ሁኑ በማለት እጆቻችንን ስናውለበልብና ወደ ኪጋሊ ስናመራ ሻለቃውን ለችሮታቸው ደጋግመን አመስግነናቸዋል፡፡
ከተወሰኑ ወራት በፊት ቢሆን ወከባ የበዛበት የሥራ ቀን ይሆን በነበረ ዕለት ቀትር ላይ ከዋና ከተማዋ ደረስን፡፡ ወደ አስፈሪው ከተማ ገባን፡፡ መንገዶቹ አልፎ አልፎ ከሚመጣው የተመድ የጭነት ተሸከርካሪ ወይም መንገድ ውር ውር ከሚሉት ከሩአግ አነስተኛ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች በስተቀር የሚንቀሳቀስ አልነበረባቸውም፡፡ ያሉትም እነዚህ ተሽከርካሪዎች በመንገዶቹ ያሉትን የሰው አስከሬኖች ወይንም ወታደሮቹ እነዚህን አስከሬኖች እንዳይበሉ በጥይት መትተው የገደሏቸውን ዉሾች ላለመዳጥ ተጠንቅቀው ይሄዳሉ፡፡ አየሩ ሞት ሞት ይሸታል፤ ንፋሱም ሰው በሌለባቸው ቤቶች ውስጥ ከሰው ላይ እንደተነሡ መናፍስት ሲሄድ ይሰማኛል፡፡ እጅግ ብዙ ሕንጻዎች በጥይትና በአዳፍኔ ተኩስ ተቃጥለውና ተበሳስተው ፈራርሰው ወድቀዋል፡፡ የሱቆች በሮች ከማጠፊያዎቻቸው ተገነጣጥለዋል፣ የዕቃ መጋዘኖችም ተዘርፈዋል፡፡ አልፎ አልፎም በርቀት ፍንዳታዎች ይሰሙናል፡፡ በአሥራዎቹ ዕድሜዬ ላይ ሆኜ ደማቅ ሰማያዊ መብራቶቿና በሰው የሚጨናነቁት መንገዶቿ ያስደመሙኝን ውቧን ከተማ በዚህ ወቅት ላውቃት አልቻልኩም፡፡
ዘዋሪው ‹‹ተጠንቅቃችሁ ተጓዙ›› ሲል አስጠነቀቀን፡፡ ‹‹በየሄዳችሁበት ፈንጂዎች ተቀብረዋል … የት የት እንደቀበርና
👍2
እንደቀበርናቸው አናስታውስም፡፡ እዚህ አካባቢ ልትላወሱ ወጥታችሁ እግራችሁን በአንድ አፍታ ልታጡ ትችላላችሁ፡፡››
የአሎይዜን ባለቤት፣ ፋሪን፣ እናገኘው እንደሆነ ብለን በቀጥታ ወደ ተመድ ዋና ጽሕፈት ቤት ነዳን፡፡ ‹‹ከኛ ቤት እስከ ተመድ በእግር የሚያስኬደው አሥራ አምስት ደቂቃ ነው፡፡ ኮርኒሳችን ውስጥ ተደብቆ ከዳነ ሊመጣ የሚችለው እዚህ ነው፡፡ ይህ ኪጋሊ ውስጥ በጣም ሰላም ያለበት ስፍራ ነው›› አለች አሎይዜ፡፡ በትልቁ የብረት በር ፊት ለፊት ቆመን አሎይዜን አወረድናት፡፡ ተንቀጠቀጠች - ካገኘኋት ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ መንፈሷ ተናወጠ፡፡ ‹‹ፋሪን ገድለውት ከሆነ እንዴት እንደምኖር አላውቅም›› ስትል እውነቱን ተናገረች፡፡ ‹‹ነፍሴ፣ ሁሉ ነገሬ ነው፣ ጥንካሬዬንም የማገኘው ከእርሱው ነው፡፡ በሕይወት እንዲኖርልኝ በጣም ስጸልይ ቆይቻለሁ… አምላክ ያንቺን ጸሎት እንደሚሰማ ሁሉ የኔንም በሰማኝ፣ ኢማኪዩሌ፡፡›› አምላክ እውነትም አሎይዜን ሰምቷት ኖሯል፡፡ ተናግራ ሳትጨርስ ያን ዓይኗ ማየት የለመደውን ሰው በግቢው ሲንቀሳቀስ አየችው፡፡ ‹‹ወይ አምላኬ … እሱው ነው! እርግጠኛ ነኝ እሱው ነው - አካሄዱን የትም ቢሆን እለየዋለሁ፡፡ ጥሩት፤ አንድ ሰው ይጥራልኝ!››
አንደኛውን የተመድ ዘበኛ ሮጦ አሎይዜ የጠቆመችበትን ሰውዬ እንዲያመጣልን ለመንነው፡፡ ሰውዬው አሎይዜን እስኪያያት ድረስ ወደኛ በቀስታ መጣ … በቻለውም መጠን ሮጠ፡፡ ዋናውን በር አልፎም በጉልበቶቹ ወደቀና ይስማት ገባ፡፡ ‹‹የኔ ውድ›› አላት፡፡ ትንንሾቹ ልጆች ኬንዛና ሳሚም ክርኖቹ ላይ ወደቁና በማቀፍና መሳም ብዛት አፈኑት፡፡ ይህ በሕይወቴ ካየኋቸው የቤተሰብ አባላት መልሰው የተገናኙባቸው ክስተቶች አንዱና እጅግ አስደሳቹ ነው፡፡ ይህ የሆነው ግን ፋሪ፣ ‹‹ሕጻኗስ?›› ብሎ እስኪጠይቅ ድረስ ብቻ ነው፡፡
የአሎይዜ ዓይኖች በእንባ ተሞሉ፡፡ ‹‹ፈጣሪ ወሰዳት›› ስትል አቃሰተች፡፡ ‹‹ትኩሳት ነበረባት፤ አልችል አለችው፡፡››
ፋሪ ራሱን በአሎይዜ ጭኖች ላይ አድርጎ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ያህል አለቀሰ፤ ሌሎቻችን በበኩላችን ተሳቀን እርስ በርሳችን እየተያየን ቆምን፡፡ አንዳችንም አሎይዜ በፈረንሳውያኑ ምሽግ ከመድረሷ በፊት ልጅ እንደሞተባት አላወቅንም፡፡ በጥንካሬዋ ተገረምን፡፡
በኋላም ፋሪ ቀና ብሎ ስለኛ ማንነት ጠየቃት፡፡ ‹‹በስደተኞች መጠለያው ልጆቼ
አድርጌ የተቀበልኳቸው እጓለማውታ›› ስትል አሎይዜ ነገረችው፡፡ ‹‹ከኛ ጋር ይቆያሉ፡፡››
‹‹እንኳን ደኅና መጣችሁልኝ›› አለ ፋሪ፡፡
‹‹ያች ረጅሟ የሮዝና የሊኦናርድ ልጅ ነች … ሁለቱም ወዳጆቻችን አርፈዋል፡፡››
‹‹ወይኔ›› አለ ፋሪ ተነሥቶ እጄን ይዞ፡፡ ‹‹ቁርጥ ወላጆችሽን የኔ ቆንጆ፡፡ ጠንክሪ - እናትና አባትሽ ቆንጆዎችና ደጋጎች ነበሩ፡፡ አንቺን አምላክ ለዓላማ ነው ያተረፈሽ… ያ ዓላማ ምን እንደሆነ እስክታውቂው ድረስ እኛ ጋ መቆየት ትችያለሽ፡፡››
‹‹አመሰግናለሁ›› ከማለት በስተቀር ምን እንደምልም አላውቅም፡፡
ወደ ተሸከርካሪው እንደገና ወጥተን ወደ አሎይዜ ቤት ሄድን፡፡ በመንገድም ላይ ሳለን ፋሪ ላለፉት አራት ወራት ቤቱን ትቶ በተመድ እንደኖረ ነገረን፡፡ ‹‹አሎይዜ ከልጆቹ ጋር ባትመለስልኝ ኖሮ›› አለ ‹‹በጭራሽ አልመለስም ነበር፡፡ ቤት እኮ ያለ ፍቅር እስር ቤት ነው፡፡››
ስፍራው ተተረማምሷል፤ መስኮቶቹ ብትንትናቸው ወጥቷል፤ ግንቡ በጥይት ተበሳስቶ፣ የጣራውም ግማሽ ክፍል ተገልጧል፡፡ ግን ሁላችንም ተረባርበን መጪውን ሳምንት ቤቱን ስንጠግንና ስናጸዳ አሳለፍን፡፡ በጥረት፣ የግንባታ እቃዎች ከተለያዩ የፈራረሱ ቤቶች ተፈልገው ስፍራው እንደገና ቤት መሰለ፡፡ ዢን ፖልና ሌሎቹ ወንዶች የራሳቸው ክፍሎች ሲደርሷቸው ፍሎረንስና እኔ በአንዷ ክፍል ተዳብለን ተቀመጥን፡፡ የወላጆቼን ቤት ከለቀቅሁ ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ አልጋ ላይ ተኛሁ፡፡ ሁላችንም ገነት ገባን!
ሻለቃ ንዋትሊ የሰጡን ምግብ ቢኖረንም ምንም ገንዘብ የለንም - ልብሶቻችን ለወራት በመለበሳቸው ነታትበዋል፡፡ ወደ ባዶ ቤቶች እየሄድን ጫማና አዳዲስ የሚለበሱ ነገሮች እንፈልግ ያዝን፡፡ በአንድ ቤት ጥንድ የወርቅ የጆሮ ጌጥ አገኘሁ፡፡ ይህን ሁሉ ካሳለፍኩ በኋላ ጥሩ እንዲሰማኝ የሚያደርግ አንድ ቆንጆ ነገር እንደሚገባኝ ራሴን አሳመንኩና ኪሴ ውስጥ አደረግኋቸው፡፡ በአሎይዜ ቤት በመስታወቱ ፊት ስሞክራቸው ግን የማየውን ምስል ልቋቋመው አልቻልኩም፡፡ የሚታየኝ የዚህ ጌጥ ባለንብረት የነበረችው ሴትዮ ፊት ብቻ ሆኖ አረፈው፡፡ የጆሮ ጌጦቹ የኔ አይደሉም፤ ምንም ትውስታዎቼም የሉባቸው፤ ሌላ ሰው እነዚህን ለማግኘት በርትታ ሰርታለች ወይንም እንደ ፍቅር ስጦታነት ተቀብላቸዋለች፡፡ በሌላ ሰው ሕይወት ውስጥ ሳይፈቀድልኝ እንደገባሁ ተሰማኝ፡፡ ለፍቼ ያላገኘኋቸውንና የማይገቡኝን ንብረቶች አልፈለኩም፤ ስለዚህ በመጭው ቀን ጌጦቹን ወዳገኘሁበት ወስጄ መለስኳቸው፡፡
በኋላም በጆሮዬ አንድ ድምፅ ያንሾካሹክ ገባ፤ በሰማሁትም በመስማማት ራሴን ነቀነቅሁ፡ ለመንቀሳቀስ ሰዓቱ አሁን ነው፡፡ ሥራ ማግኛ ጊዜዬ አሁን ነች፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
የአሎይዜን ባለቤት፣ ፋሪን፣ እናገኘው እንደሆነ ብለን በቀጥታ ወደ ተመድ ዋና ጽሕፈት ቤት ነዳን፡፡ ‹‹ከኛ ቤት እስከ ተመድ በእግር የሚያስኬደው አሥራ አምስት ደቂቃ ነው፡፡ ኮርኒሳችን ውስጥ ተደብቆ ከዳነ ሊመጣ የሚችለው እዚህ ነው፡፡ ይህ ኪጋሊ ውስጥ በጣም ሰላም ያለበት ስፍራ ነው›› አለች አሎይዜ፡፡ በትልቁ የብረት በር ፊት ለፊት ቆመን አሎይዜን አወረድናት፡፡ ተንቀጠቀጠች - ካገኘኋት ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ መንፈሷ ተናወጠ፡፡ ‹‹ፋሪን ገድለውት ከሆነ እንዴት እንደምኖር አላውቅም›› ስትል እውነቱን ተናገረች፡፡ ‹‹ነፍሴ፣ ሁሉ ነገሬ ነው፣ ጥንካሬዬንም የማገኘው ከእርሱው ነው፡፡ በሕይወት እንዲኖርልኝ በጣም ስጸልይ ቆይቻለሁ… አምላክ ያንቺን ጸሎት እንደሚሰማ ሁሉ የኔንም በሰማኝ፣ ኢማኪዩሌ፡፡›› አምላክ እውነትም አሎይዜን ሰምቷት ኖሯል፡፡ ተናግራ ሳትጨርስ ያን ዓይኗ ማየት የለመደውን ሰው በግቢው ሲንቀሳቀስ አየችው፡፡ ‹‹ወይ አምላኬ … እሱው ነው! እርግጠኛ ነኝ እሱው ነው - አካሄዱን የትም ቢሆን እለየዋለሁ፡፡ ጥሩት፤ አንድ ሰው ይጥራልኝ!››
አንደኛውን የተመድ ዘበኛ ሮጦ አሎይዜ የጠቆመችበትን ሰውዬ እንዲያመጣልን ለመንነው፡፡ ሰውዬው አሎይዜን እስኪያያት ድረስ ወደኛ በቀስታ መጣ … በቻለውም መጠን ሮጠ፡፡ ዋናውን በር አልፎም በጉልበቶቹ ወደቀና ይስማት ገባ፡፡ ‹‹የኔ ውድ›› አላት፡፡ ትንንሾቹ ልጆች ኬንዛና ሳሚም ክርኖቹ ላይ ወደቁና በማቀፍና መሳም ብዛት አፈኑት፡፡ ይህ በሕይወቴ ካየኋቸው የቤተሰብ አባላት መልሰው የተገናኙባቸው ክስተቶች አንዱና እጅግ አስደሳቹ ነው፡፡ ይህ የሆነው ግን ፋሪ፣ ‹‹ሕጻኗስ?›› ብሎ እስኪጠይቅ ድረስ ብቻ ነው፡፡
የአሎይዜ ዓይኖች በእንባ ተሞሉ፡፡ ‹‹ፈጣሪ ወሰዳት›› ስትል አቃሰተች፡፡ ‹‹ትኩሳት ነበረባት፤ አልችል አለችው፡፡››
ፋሪ ራሱን በአሎይዜ ጭኖች ላይ አድርጎ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ ያህል አለቀሰ፤ ሌሎቻችን በበኩላችን ተሳቀን እርስ በርሳችን እየተያየን ቆምን፡፡ አንዳችንም አሎይዜ በፈረንሳውያኑ ምሽግ ከመድረሷ በፊት ልጅ እንደሞተባት አላወቅንም፡፡ በጥንካሬዋ ተገረምን፡፡
በኋላም ፋሪ ቀና ብሎ ስለኛ ማንነት ጠየቃት፡፡ ‹‹በስደተኞች መጠለያው ልጆቼ
አድርጌ የተቀበልኳቸው እጓለማውታ›› ስትል አሎይዜ ነገረችው፡፡ ‹‹ከኛ ጋር ይቆያሉ፡፡››
‹‹እንኳን ደኅና መጣችሁልኝ›› አለ ፋሪ፡፡
‹‹ያች ረጅሟ የሮዝና የሊኦናርድ ልጅ ነች … ሁለቱም ወዳጆቻችን አርፈዋል፡፡››
‹‹ወይኔ›› አለ ፋሪ ተነሥቶ እጄን ይዞ፡፡ ‹‹ቁርጥ ወላጆችሽን የኔ ቆንጆ፡፡ ጠንክሪ - እናትና አባትሽ ቆንጆዎችና ደጋጎች ነበሩ፡፡ አንቺን አምላክ ለዓላማ ነው ያተረፈሽ… ያ ዓላማ ምን እንደሆነ እስክታውቂው ድረስ እኛ ጋ መቆየት ትችያለሽ፡፡››
‹‹አመሰግናለሁ›› ከማለት በስተቀር ምን እንደምልም አላውቅም፡፡
ወደ ተሸከርካሪው እንደገና ወጥተን ወደ አሎይዜ ቤት ሄድን፡፡ በመንገድም ላይ ሳለን ፋሪ ላለፉት አራት ወራት ቤቱን ትቶ በተመድ እንደኖረ ነገረን፡፡ ‹‹አሎይዜ ከልጆቹ ጋር ባትመለስልኝ ኖሮ›› አለ ‹‹በጭራሽ አልመለስም ነበር፡፡ ቤት እኮ ያለ ፍቅር እስር ቤት ነው፡፡››
ስፍራው ተተረማምሷል፤ መስኮቶቹ ብትንትናቸው ወጥቷል፤ ግንቡ በጥይት ተበሳስቶ፣ የጣራውም ግማሽ ክፍል ተገልጧል፡፡ ግን ሁላችንም ተረባርበን መጪውን ሳምንት ቤቱን ስንጠግንና ስናጸዳ አሳለፍን፡፡ በጥረት፣ የግንባታ እቃዎች ከተለያዩ የፈራረሱ ቤቶች ተፈልገው ስፍራው እንደገና ቤት መሰለ፡፡ ዢን ፖልና ሌሎቹ ወንዶች የራሳቸው ክፍሎች ሲደርሷቸው ፍሎረንስና እኔ በአንዷ ክፍል ተዳብለን ተቀመጥን፡፡ የወላጆቼን ቤት ከለቀቅሁ ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ አልጋ ላይ ተኛሁ፡፡ ሁላችንም ገነት ገባን!
ሻለቃ ንዋትሊ የሰጡን ምግብ ቢኖረንም ምንም ገንዘብ የለንም - ልብሶቻችን ለወራት በመለበሳቸው ነታትበዋል፡፡ ወደ ባዶ ቤቶች እየሄድን ጫማና አዳዲስ የሚለበሱ ነገሮች እንፈልግ ያዝን፡፡ በአንድ ቤት ጥንድ የወርቅ የጆሮ ጌጥ አገኘሁ፡፡ ይህን ሁሉ ካሳለፍኩ በኋላ ጥሩ እንዲሰማኝ የሚያደርግ አንድ ቆንጆ ነገር እንደሚገባኝ ራሴን አሳመንኩና ኪሴ ውስጥ አደረግኋቸው፡፡ በአሎይዜ ቤት በመስታወቱ ፊት ስሞክራቸው ግን የማየውን ምስል ልቋቋመው አልቻልኩም፡፡ የሚታየኝ የዚህ ጌጥ ባለንብረት የነበረችው ሴትዮ ፊት ብቻ ሆኖ አረፈው፡፡ የጆሮ ጌጦቹ የኔ አይደሉም፤ ምንም ትውስታዎቼም የሉባቸው፤ ሌላ ሰው እነዚህን ለማግኘት በርትታ ሰርታለች ወይንም እንደ ፍቅር ስጦታነት ተቀብላቸዋለች፡፡ በሌላ ሰው ሕይወት ውስጥ ሳይፈቀድልኝ እንደገባሁ ተሰማኝ፡፡ ለፍቼ ያላገኘኋቸውንና የማይገቡኝን ንብረቶች አልፈለኩም፤ ስለዚህ በመጭው ቀን ጌጦቹን ወዳገኘሁበት ወስጄ መለስኳቸው፡፡
በኋላም በጆሮዬ አንድ ድምፅ ያንሾካሹክ ገባ፤ በሰማሁትም በመስማማት ራሴን ነቀነቅሁ፡ ለመንቀሳቀስ ሰዓቱ አሁን ነው፡፡ ሥራ ማግኛ ጊዜዬ አሁን ነች፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3