‹‹ያው አብረን በቆየንባቸው ጊዜቶች በተናጠልም ሆነ አንድ ላይ በተጫወትናቸው ጫወታዎች ወዲፊት ምኞታችሁንና ህልማችሁን ለመረዳት ችያለው፡፡ለምሳሌ የኑሀሚ ዋናው ህልም የወላጆቻችሁን በግፍ የተነጠቀ ቢላ ቤት በሆነ መንገድ ማስመለስ ነው.፡፡የናኦል ደግሞ ሀብታም ሆኖ እህቱን መንከባከብና ምንም አይነት ችግር እዳይገጥማት ማድረግ ነው..ተሳሳትኩ፡፡››
‹‹አረ ትክክል ነሽ፡፡››ሁለቱም በጋራ መለሱላት፡፡
‹‹ይሄንን ምኞታችሁን ለማሳካት ምን ያህል መስዋእትነት ለመክፈል ፍቃደኛ ናችሁ?››
‹‹እኔ ሙሉ አዲስአበባን ማቃጠል ካለብኝ አቃጥላለው››አለች ኑሀሚ፡፡
‹‹እኔም አደርገዋለው›› መለሰ ናኦል፡፡
‹‹አዲስ አበባን ማቃጠል አይጠበቅባችሁም…እናንተ ጠንካራ ፤ሚስጥር ጠባቂ፤ታታሪና ከሆናችሁ ይሄንን ህልማችሁን እውን ለማድረግ እንድትችሉ እኔ ልረዳችሁ እችላለሁ..››
‹‹እንዴ እህቴ እውነትሽን ነው…?ያልሺኝን እናደርጋለን፤ካንቺ ቃል ውልፍች አንልም፡፡››
ፊቷን ወደ ኑሀሚ አዞረችና የሆነ ነገር እንድትል ትጠብቃት ጀመር…..ኑሀሚ ረዘም ያለ ደቂቃ ስትተክዝ ቆየችና እንባዋን እያንጠባጠበች‹‹…ለእኔ ያንን የወላጆቼን ቤት መልሶ ማግኘት ገነት የመግባት ያህል ነው የምጓጓለት፡፡እሱን መልሰን የራሳችን እንድናደርግ ከረዳሺን ምንም ነገር ብትይን ምንም ያለማወላወል እንደምናደርገው እርግጠኛ ሁኚ፡፡››
‹‹ጥሩ ….እንደዛ ከሆነ የምትፈልጉት ነገር ለማግኘት በጣም ጠንካራ ተፋላሚና ባለስል አእምሮ ባለቤት መሆን አለባችሁ፡፡ለዚህ እንዲረዳችሁ የሆነ የመንግስት ተቋም ከ10-15 ዓመት እድሜ ያላቸውን ታዳጊዎችን ወስዶ ሚስጥራዊ በሆነ ስፋራ ሁለገብ የሆነ ስልጠና ይሰጣል፡፡ስልጠናው የሚወስደው ለ5 አመት ነው፡፡በ5 አመት ውስጥ መደበኛ ትምህርት ትማራላችሁ፤ቋንቋ ትማራላችሁ፤ወታደራዊ ስልጠና ትወስዳላችሁ፤ከዛ እንደብቃታችሁ በተለያየ የመንግስት ተቋማት ውስጥ ትመደባላችሁ፡፡በተለይ ከ80 ሰልጣኞች መካከል ከ1- 20 ደረጃ ይዛችሁ ካጠናቀቃችሁ….በጣም ልዩ የተባለ እድል ነዋ የሚያጋጥማችሁ፡፡አንድ ማወቅ ያለባችሁ ነገር ግን ሰልጠናውን ለ5 አመት ከወሰደችሁ በኃላ ለአስር አመት የማገልገል ግዴታ አለባችሁ፡፡››
‹‹እህቴ የምትይው ነገር ያጓጓል….ግን የምንችለው ይመስልሻል?››ናኦል በጥርጣሬ ጠየቀ፡፡
‹‹ባይመስለኝማ ለዚህ ስራ አላጫችሁም ነበር››
‹‹እኔ ያልገባኝ…ይሄ ያልሽው የትምህርት ፤የቋንቋ ጥናት፤ ወታደራዊ ስልጠና…ስራ ለማግኘት ሊረዳን ይችላላል..?ማለት ፖሊስ ምናምን ልንሆን እንችላለን?እሺ እሱ ይሁን..ግን እንዴት አድርጎ ነው ቤታችንን የምናስመልሰው ?ሀብታምስ የምንሆነው?፡፡››ስትል ኑሀሚ እንደወትሮዋ ጠጠር ያለውን ጥያቄ ጠየቀቻት፡፡
‹‹አይ ፖሊስ አትሆኑም…እንዳልኮችሁ ከ1-20 ከወጣችሁ ለሌላ የስለላ ስልጠና ወደውጭ ሀገር ትሄዱና ለተጨማሪ ሁለት ሶስት አመት የስለላ ትምህርት ትወስዱና ተመለሳችሁ፡፡በሀገሪቱ ከፍተኛ የደህንነት መስሪያ ቤት ውስጥ ሰላይ ሆናችሁ ታገለግላላችሁ፡፡ደረጃችሁ ከ20 በታችም ከሆነ ያው እደየችሎታችሁ ተመሳሳይ አይነት ሚስጥራዊ ስራዎችን ለሀገሪቱ ትሰራላችሁ…እቤቱን ባልሽው እመኚኝ በቀላሉ ይሳካል፡፡ ሰውዬው ላይ ሙሉ ምርመራ ይከፈታል ፤ መረጃዎች ከእንደገና ይታያሉ፤ፍርድ ቤትም ሳይሄድ ሰውዬው በፍላጎቱ ቤቱን አስረክቦ እንዲለቅ ማድረግ ይቻላል፡፡በተለይ እንዳልኳችሁ ቢያንስ ከሁለት አንዳችሁ ከ1-20 ውስጥ ከወጣችሁ የቤቱን ጉዳይ በእርግጠኝነት ይሳካል፡፡ሀብታም መሆኑን ያልኮችሁ ግን እንደእናንተ ብልጠትና ጥንካሬ የሚወሰን ነው፡፡ያንን እርግጠኛ ሆኜ ቃሌን ልሰጣችሁ አልችልም፡፡፡››
‹‹ገባኝ እሺ…ግን አንቺ ይሄንን እንዴት አወቅሽ?››
‹‹እኔም ተመሳሳይ ስልጠና ወስጄ ተመሳሳይ ስራ ምሰራ የስለላ ባለሞያ በመሆኔ ነው በእርግጠኝነት እየነገርኳችሁ ያለሁት››
ኑሀሚ እንጣጥ ብላ ከተቀመጠችበት ተነሳች..‹‹አውቄው ነበር፤የሆነ ነገር እንደደበቅሽን እርግጠኛ ነበርኩ..አየህ ወንድሜ ለወደፊቱ ትምህርት ይሁንህ …ዝም ብለህ ሰውን በቀላሉ አትመን፡፡››
ናኦል የእህቱ እንደ እብድ መሆንና ከአንደበቷ ምትሰነዝራቸው ንግግሮች ምስራቅን እንዳያስቀይም በመፍራት በተቀመጠበት ተቁነጠነጠ፡፡ምስራቅ መናገር ጀመረ..‹‹እኔም ለዚህ ስራ ፐርፌክት እንደምትሆኚ እርግጠኛ የሆንኩት ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ነው፡፡ይሄ ተጣራጣሪነትሽ….ነገሮችን ከስር መሰረቱ አብጠርጥሮ ለመረዳት ያለሽ ተነሳሽነት፤አካባቢሽን ለመረዳት የምታደርጊው ጥረት….ወደፊት እንዲህ ቢሆን ብለሽ መተንበይና መተንተን ችሎታሽ ከእድሜሽ በጣም የራቀና የበሰለ በመሆኑ በተፈጥሮ ለዚህ ስራ የተሰጠሸ መሆንሽ ምልክት ነው፡፡እመኚኝ በጣም ነው ሚሳካልሽ፡፡››
‹‹እኔስ አይሳካልኝም ማለት ነው?፡፡››ቅሬታ ባዘለ የድምፅ ቃና ጥያቄውን ያቀረበው ናኦል ነበር፡፡
ምስራቅ ፈገግ አለች‹‹እውነት ለመናገር አንተም የራስ የሆኑ ኳሊቲዎች አሉህ…ታናሽ እህትህ ግን በዚህ ጉዳይ ላይ በጣም የተለየች ነች ለማለት ፈልጌ ነው፡፡ለማንኛው አሁን ክፍላችሁ ግቡና ተመካከሩ ፡፡ ከመተኛታችሁ በፊት ውሳኔያችሁን መጥታችሁ አሳውቁኝ፤እስከዛ ፊልም እያየሁ ጠብቃችኋለው፡፡
‹‹እንዴ…ዛሬውኑ?››
‹‹አዎ አሁን…አንድ ሰዓት ካሰባችሁበትና ከተማከራችሁበት በቂ ነው…ከተስማማችሁ በለሊት እወስድና አሰረክባችኋለው፡፡››
‹‹ምንድነው እንደዚህ ጥድፊያው?››ኑሀሚ ነች ጠያቂዋ፡፡
‹‹እንግዲህ አሰራሩ እንደዚህ ነው….በሉ ተነሱ ግቡ››
‹‹እህቴ ተስማምተን ከሄድን ግን አንቺም አብሪሽን ትሆኚያለሽ?››
ናሆም ምስራቅን በስስት እየተመለከተ ጠየቃት፡፡
ምስረቅ ፈገግ አለች‹‹አይ አልችልም…ጨርሳችሁ ስትወጡ ግን የምቀበላችሁ እኔው እራሴ ነኝ››ስትል ነበር ቃል የገባችላቸው፡፡
‹‹እኔ አምስት አመት ሙሉ አንቺን ሳላይ …እንዴት?››
‹‹ወረኛ ከአምስት ወራት በፊት እኮ ጭራሽ እስከመፈጠሯ አታውቃትም ነበር….በል ና እንግባ››ኑሀሚ አበሻቀጠችው፡፡ተያይዘው ገቡ፡፡መኝታ ቤታቸው ዘግተው አልጋው ጠርዝ ላይ ጎን ለጎን ተቀመጡ፡፡ለሀያ ደቂቃ ሁለቱም እርስ በርስ መነጋገር አልቻሉም ነበር፡፡
‹‹እህቴ ዝም አልሽ..የሆነ ነገር በያ››ናሆም በፍራቻ ውስጥ ሆኖ ጠየቃት፡፡
‹‹ምን እላለሁ….ነገሩ ምንም ግልፅ አይደለም፤የተወሳሰበ የማፊያ አይነት ስራ ነው የሚመስለው፡፡››
‹‹ግን እውነት ለመንግስት ምትሰራ ይመስልሻል?››
‹‹አንተም ተጠራጠርካት አይደል?ለመንግስትም ይሁን ለሌለ አላውቅም ግን ለሆነ ግብዳ ተቋም እንደምትሰራ እርግጥ ነው፡፡ህይወት እንድትበራልን ከፈለግን ጨከን ብለን እንዲህ አይነት ነገሮችን መሞከር አለብን፡፡ለመንግስትም ሆነ ለማፍዬዎች ለእኛ ምን ለውጥ አለው..?መንግስት ለእኛ ምን አድረጎልናል?››
‹‹አይ ማለት ለደህነነታችን ብዬ ነዋ፡፡››
‹‹ያው ነው ..ካበሳጨነው መንግስትም ይገድልኸል.. ማፊያዎቹም ይገድሉሀል…ዋናው እስማርት መሆንና የጨዌውን ህግ ጠንቅቆ በማወቅ በህጉ መሰረት መጫወት ነው፡፡››
‹‹እና እንሳማማ እያልሺኝ ነው?፡፡››
‹‹አዎ ሌላ ምርጫ እኮ የለንም…››
‹‹እንዴ ምን ማለትሽ ነው…?እምቢ ብለን እኮ እሷን አመስግነን እቤቷን ለቀን ወደምንሄድበት መሄድ እንችላለን፡፡››
‹‹አንችልም፡፡››
‹‹አረ ትክክል ነሽ፡፡››ሁለቱም በጋራ መለሱላት፡፡
‹‹ይሄንን ምኞታችሁን ለማሳካት ምን ያህል መስዋእትነት ለመክፈል ፍቃደኛ ናችሁ?››
‹‹እኔ ሙሉ አዲስአበባን ማቃጠል ካለብኝ አቃጥላለው››አለች ኑሀሚ፡፡
‹‹እኔም አደርገዋለው›› መለሰ ናኦል፡፡
‹‹አዲስ አበባን ማቃጠል አይጠበቅባችሁም…እናንተ ጠንካራ ፤ሚስጥር ጠባቂ፤ታታሪና ከሆናችሁ ይሄንን ህልማችሁን እውን ለማድረግ እንድትችሉ እኔ ልረዳችሁ እችላለሁ..››
‹‹እንዴ እህቴ እውነትሽን ነው…?ያልሺኝን እናደርጋለን፤ካንቺ ቃል ውልፍች አንልም፡፡››
ፊቷን ወደ ኑሀሚ አዞረችና የሆነ ነገር እንድትል ትጠብቃት ጀመር…..ኑሀሚ ረዘም ያለ ደቂቃ ስትተክዝ ቆየችና እንባዋን እያንጠባጠበች‹‹…ለእኔ ያንን የወላጆቼን ቤት መልሶ ማግኘት ገነት የመግባት ያህል ነው የምጓጓለት፡፡እሱን መልሰን የራሳችን እንድናደርግ ከረዳሺን ምንም ነገር ብትይን ምንም ያለማወላወል እንደምናደርገው እርግጠኛ ሁኚ፡፡››
‹‹ጥሩ ….እንደዛ ከሆነ የምትፈልጉት ነገር ለማግኘት በጣም ጠንካራ ተፋላሚና ባለስል አእምሮ ባለቤት መሆን አለባችሁ፡፡ለዚህ እንዲረዳችሁ የሆነ የመንግስት ተቋም ከ10-15 ዓመት እድሜ ያላቸውን ታዳጊዎችን ወስዶ ሚስጥራዊ በሆነ ስፋራ ሁለገብ የሆነ ስልጠና ይሰጣል፡፡ስልጠናው የሚወስደው ለ5 አመት ነው፡፡በ5 አመት ውስጥ መደበኛ ትምህርት ትማራላችሁ፤ቋንቋ ትማራላችሁ፤ወታደራዊ ስልጠና ትወስዳላችሁ፤ከዛ እንደብቃታችሁ በተለያየ የመንግስት ተቋማት ውስጥ ትመደባላችሁ፡፡በተለይ ከ80 ሰልጣኞች መካከል ከ1- 20 ደረጃ ይዛችሁ ካጠናቀቃችሁ….በጣም ልዩ የተባለ እድል ነዋ የሚያጋጥማችሁ፡፡አንድ ማወቅ ያለባችሁ ነገር ግን ሰልጠናውን ለ5 አመት ከወሰደችሁ በኃላ ለአስር አመት የማገልገል ግዴታ አለባችሁ፡፡››
‹‹እህቴ የምትይው ነገር ያጓጓል….ግን የምንችለው ይመስልሻል?››ናኦል በጥርጣሬ ጠየቀ፡፡
‹‹ባይመስለኝማ ለዚህ ስራ አላጫችሁም ነበር››
‹‹እኔ ያልገባኝ…ይሄ ያልሽው የትምህርት ፤የቋንቋ ጥናት፤ ወታደራዊ ስልጠና…ስራ ለማግኘት ሊረዳን ይችላላል..?ማለት ፖሊስ ምናምን ልንሆን እንችላለን?እሺ እሱ ይሁን..ግን እንዴት አድርጎ ነው ቤታችንን የምናስመልሰው ?ሀብታምስ የምንሆነው?፡፡››ስትል ኑሀሚ እንደወትሮዋ ጠጠር ያለውን ጥያቄ ጠየቀቻት፡፡
‹‹አይ ፖሊስ አትሆኑም…እንዳልኮችሁ ከ1-20 ከወጣችሁ ለሌላ የስለላ ስልጠና ወደውጭ ሀገር ትሄዱና ለተጨማሪ ሁለት ሶስት አመት የስለላ ትምህርት ትወስዱና ተመለሳችሁ፡፡በሀገሪቱ ከፍተኛ የደህንነት መስሪያ ቤት ውስጥ ሰላይ ሆናችሁ ታገለግላላችሁ፡፡ደረጃችሁ ከ20 በታችም ከሆነ ያው እደየችሎታችሁ ተመሳሳይ አይነት ሚስጥራዊ ስራዎችን ለሀገሪቱ ትሰራላችሁ…እቤቱን ባልሽው እመኚኝ በቀላሉ ይሳካል፡፡ ሰውዬው ላይ ሙሉ ምርመራ ይከፈታል ፤ መረጃዎች ከእንደገና ይታያሉ፤ፍርድ ቤትም ሳይሄድ ሰውዬው በፍላጎቱ ቤቱን አስረክቦ እንዲለቅ ማድረግ ይቻላል፡፡በተለይ እንዳልኳችሁ ቢያንስ ከሁለት አንዳችሁ ከ1-20 ውስጥ ከወጣችሁ የቤቱን ጉዳይ በእርግጠኝነት ይሳካል፡፡ሀብታም መሆኑን ያልኮችሁ ግን እንደእናንተ ብልጠትና ጥንካሬ የሚወሰን ነው፡፡ያንን እርግጠኛ ሆኜ ቃሌን ልሰጣችሁ አልችልም፡፡፡››
‹‹ገባኝ እሺ…ግን አንቺ ይሄንን እንዴት አወቅሽ?››
‹‹እኔም ተመሳሳይ ስልጠና ወስጄ ተመሳሳይ ስራ ምሰራ የስለላ ባለሞያ በመሆኔ ነው በእርግጠኝነት እየነገርኳችሁ ያለሁት››
ኑሀሚ እንጣጥ ብላ ከተቀመጠችበት ተነሳች..‹‹አውቄው ነበር፤የሆነ ነገር እንደደበቅሽን እርግጠኛ ነበርኩ..አየህ ወንድሜ ለወደፊቱ ትምህርት ይሁንህ …ዝም ብለህ ሰውን በቀላሉ አትመን፡፡››
ናኦል የእህቱ እንደ እብድ መሆንና ከአንደበቷ ምትሰነዝራቸው ንግግሮች ምስራቅን እንዳያስቀይም በመፍራት በተቀመጠበት ተቁነጠነጠ፡፡ምስራቅ መናገር ጀመረ..‹‹እኔም ለዚህ ስራ ፐርፌክት እንደምትሆኚ እርግጠኛ የሆንኩት ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ነው፡፡ይሄ ተጣራጣሪነትሽ….ነገሮችን ከስር መሰረቱ አብጠርጥሮ ለመረዳት ያለሽ ተነሳሽነት፤አካባቢሽን ለመረዳት የምታደርጊው ጥረት….ወደፊት እንዲህ ቢሆን ብለሽ መተንበይና መተንተን ችሎታሽ ከእድሜሽ በጣም የራቀና የበሰለ በመሆኑ በተፈጥሮ ለዚህ ስራ የተሰጠሸ መሆንሽ ምልክት ነው፡፡እመኚኝ በጣም ነው ሚሳካልሽ፡፡››
‹‹እኔስ አይሳካልኝም ማለት ነው?፡፡››ቅሬታ ባዘለ የድምፅ ቃና ጥያቄውን ያቀረበው ናኦል ነበር፡፡
ምስራቅ ፈገግ አለች‹‹እውነት ለመናገር አንተም የራስ የሆኑ ኳሊቲዎች አሉህ…ታናሽ እህትህ ግን በዚህ ጉዳይ ላይ በጣም የተለየች ነች ለማለት ፈልጌ ነው፡፡ለማንኛው አሁን ክፍላችሁ ግቡና ተመካከሩ ፡፡ ከመተኛታችሁ በፊት ውሳኔያችሁን መጥታችሁ አሳውቁኝ፤እስከዛ ፊልም እያየሁ ጠብቃችኋለው፡፡
‹‹እንዴ…ዛሬውኑ?››
‹‹አዎ አሁን…አንድ ሰዓት ካሰባችሁበትና ከተማከራችሁበት በቂ ነው…ከተስማማችሁ በለሊት እወስድና አሰረክባችኋለው፡፡››
‹‹ምንድነው እንደዚህ ጥድፊያው?››ኑሀሚ ነች ጠያቂዋ፡፡
‹‹እንግዲህ አሰራሩ እንደዚህ ነው….በሉ ተነሱ ግቡ››
‹‹እህቴ ተስማምተን ከሄድን ግን አንቺም አብሪሽን ትሆኚያለሽ?››
ናሆም ምስራቅን በስስት እየተመለከተ ጠየቃት፡፡
ምስረቅ ፈገግ አለች‹‹አይ አልችልም…ጨርሳችሁ ስትወጡ ግን የምቀበላችሁ እኔው እራሴ ነኝ››ስትል ነበር ቃል የገባችላቸው፡፡
‹‹እኔ አምስት አመት ሙሉ አንቺን ሳላይ …እንዴት?››
‹‹ወረኛ ከአምስት ወራት በፊት እኮ ጭራሽ እስከመፈጠሯ አታውቃትም ነበር….በል ና እንግባ››ኑሀሚ አበሻቀጠችው፡፡ተያይዘው ገቡ፡፡መኝታ ቤታቸው ዘግተው አልጋው ጠርዝ ላይ ጎን ለጎን ተቀመጡ፡፡ለሀያ ደቂቃ ሁለቱም እርስ በርስ መነጋገር አልቻሉም ነበር፡፡
‹‹እህቴ ዝም አልሽ..የሆነ ነገር በያ››ናሆም በፍራቻ ውስጥ ሆኖ ጠየቃት፡፡
‹‹ምን እላለሁ….ነገሩ ምንም ግልፅ አይደለም፤የተወሳሰበ የማፊያ አይነት ስራ ነው የሚመስለው፡፡››
‹‹ግን እውነት ለመንግስት ምትሰራ ይመስልሻል?››
‹‹አንተም ተጠራጠርካት አይደል?ለመንግስትም ይሁን ለሌለ አላውቅም ግን ለሆነ ግብዳ ተቋም እንደምትሰራ እርግጥ ነው፡፡ህይወት እንድትበራልን ከፈለግን ጨከን ብለን እንዲህ አይነት ነገሮችን መሞከር አለብን፡፡ለመንግስትም ሆነ ለማፍዬዎች ለእኛ ምን ለውጥ አለው..?መንግስት ለእኛ ምን አድረጎልናል?››
‹‹አይ ማለት ለደህነነታችን ብዬ ነዋ፡፡››
‹‹ያው ነው ..ካበሳጨነው መንግስትም ይገድልኸል.. ማፊያዎቹም ይገድሉሀል…ዋናው እስማርት መሆንና የጨዌውን ህግ ጠንቅቆ በማወቅ በህጉ መሰረት መጫወት ነው፡፡››
‹‹እና እንሳማማ እያልሺኝ ነው?፡፡››
‹‹አዎ ሌላ ምርጫ እኮ የለንም…››
‹‹እንዴ ምን ማለትሽ ነው…?እምቢ ብለን እኮ እሷን አመስግነን እቤቷን ለቀን ወደምንሄድበት መሄድ እንችላለን፡፡››
‹‹አንችልም፡፡››
👍54❤7👏3
ናኦል በእህቱ መልስ ግራ ተጋባ፡፡እሷ ከመቀመጫዋ ተነሳችና ወደመስኮት ሄደች፡፡ቀስ ብላ የመጋረጃውን አካፋይ ላይ ከፈት አደረገችና አይኖቾን አጨንቁራ ወደ ታች ተመለከተች…‹‹ና እስቲ››
ምን ልታሳየው እንደሆነ ባይገባውም ከተቀመጠበት ተነሳና ሄደ.. እሷ እንደምታደርገው አይኖቹን አጨንቁሮ ተመለከተ፡፡‹‹ ያቺን ጥቁር መኪና አየሀት…እኛን መከተል ከጀመረች ሳምንት ሆናት፤እንዳትፈራ ብዬ አልነገርኩህም እንጂ ወደከታማ ስንሄድ በሔድንበት ሁሉ እየሄዱ ሲከተሉን ነበር፡፡ወንድሜ የገባንበት ወጥመድ እንዲህ ቀላል አይደለም፡፡ይህቺ ያንተ ተመራጭ ምስራቅም እንደምታያት ቀላል ሴት አይደለችም፡፡እኛ ደግሞ ስለእሷ የሆኑ የሆኑ ነገሮችን ነቄ ብለናል..አሁን ባቀረበችልን ሀሳብ አንስማማን ብለን እንንካው ብንላት…ዝም ብለው በቃ ቸው ብለው ሚሸኙን ይመስልሀል..አታስበው››
ናኦል እርግጠኝነት በማይነበብበት ስሜት ‹‹አረ እህቴ ምስራቅ በእኛ ላይ እንዲህ ታደርጋለች››በማለት ሊሞግታት ፈለገ፡፡
‹‹አይ ይሄ እኮ የስራው ፀባይ ነው፡፡የስጋ ወንድም እህቶቾም ብንሆን ተመሳሳዩን ነው የምታደርገው፡፡በል ተነስና አሁን የነገርኩህን ነገሮች በሆድህ አስቀምጠህ ባቀረበችልን ሀሳብ መስማማታችንን እንንገራትና ለሊት ወደሚወስዱን ቦታ ለመሄድ ዝግጁ እንሁን፡፡››
ተስማሙና ወደሳሎን ሄደው መሳማማታቸው ነገሯት፡፡በደስታ ከተቀመጠችበት ተነሳታ አቀፈቻቸውና ሁለቱንማ ሳመቻቸው፡፡አንስማማም ቢሉ ስለሚሆነው ነገር እንደተጨነቀች ከሁኔታዋ ያሳታውቃል፡፡ እንደተባለውም ጥዋት ወስዳቸው ፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ምን ልታሳየው እንደሆነ ባይገባውም ከተቀመጠበት ተነሳና ሄደ.. እሷ እንደምታደርገው አይኖቹን አጨንቁሮ ተመለከተ፡፡‹‹ ያቺን ጥቁር መኪና አየሀት…እኛን መከተል ከጀመረች ሳምንት ሆናት፤እንዳትፈራ ብዬ አልነገርኩህም እንጂ ወደከታማ ስንሄድ በሔድንበት ሁሉ እየሄዱ ሲከተሉን ነበር፡፡ወንድሜ የገባንበት ወጥመድ እንዲህ ቀላል አይደለም፡፡ይህቺ ያንተ ተመራጭ ምስራቅም እንደምታያት ቀላል ሴት አይደለችም፡፡እኛ ደግሞ ስለእሷ የሆኑ የሆኑ ነገሮችን ነቄ ብለናል..አሁን ባቀረበችልን ሀሳብ አንስማማን ብለን እንንካው ብንላት…ዝም ብለው በቃ ቸው ብለው ሚሸኙን ይመስልሀል..አታስበው››
ናኦል እርግጠኝነት በማይነበብበት ስሜት ‹‹አረ እህቴ ምስራቅ በእኛ ላይ እንዲህ ታደርጋለች››በማለት ሊሞግታት ፈለገ፡፡
‹‹አይ ይሄ እኮ የስራው ፀባይ ነው፡፡የስጋ ወንድም እህቶቾም ብንሆን ተመሳሳዩን ነው የምታደርገው፡፡በል ተነስና አሁን የነገርኩህን ነገሮች በሆድህ አስቀምጠህ ባቀረበችልን ሀሳብ መስማማታችንን እንንገራትና ለሊት ወደሚወስዱን ቦታ ለመሄድ ዝግጁ እንሁን፡፡››
ተስማሙና ወደሳሎን ሄደው መሳማማታቸው ነገሯት፡፡በደስታ ከተቀመጠችበት ተነሳታ አቀፈቻቸውና ሁለቱንማ ሳመቻቸው፡፡አንስማማም ቢሉ ስለሚሆነው ነገር እንደተጨነቀች ከሁኔታዋ ያሳታውቃል፡፡ እንደተባለውም ጥዋት ወስዳቸው ፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍61🥰17❤6👏4🤔1
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ከምስራቅ ካር ስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ይገጥመናል ከሉት በላይ በጣም የተወሳሰበ ነገር ነበር የገጠማቸው፡፡በመጀመሪያ የት እንደተወሰዱ ያለማወቃቸው ነበር ከባድ ነገር፡፡ መስታወቱ ድፍን ጥቁር ሆኖ ወደውጭ በማያሳይ መኪና ውስጥ ተከተው…ለአንድ ሰዓት ለበለጠ ጊዜ ሲጓዙ ከቆ በኃላ መኪናዋ ቆመችና ሲወርዱ አምስት የሚሆኑ ባለአምስት ፎቅ ዘመናው ህንፃዎች ያሉበት የእግር ኳስ መጫወቻ ሜዳ፤ የመረብ ኳስ እና የመሳሰሉት ሜዳዎች ያሉበት ዙሪያውን በደን የተሸፈነ እና ቢያንስ 3 ሜትር ሚሆን ከኮንክሪትና ከብሎኬት የተሰራ አጥር ….በአጥሩ ጫፍ ላይ አደገኛ ሽቦ የተጠመጠመበት በጣም አስፈሪ ድባብ የተላበሰ ግዙፍ ስፍራ ነው፡፡በዛ ላይ .በተወሰነ ሜትር ርቀት በየሰዓቱ በሚቀያየሩ ቆፍጣና የጥበቃ ወታደሮች የሚታዩበት አስፈሪ ግቢ ውስጥ ነው ይዘዋቸው የገቡት፡፡
ይዞቸው ከመጡት መካከል አንድ ወደአንደኛው ፎቅ ይዟቸው ሄደና ወዳአንድ ቢሮ አስገባቸውና ምንነቱን ያለወቁት የሆነ ወረቀት አስፈርሞ በማስረከብ ቀሪውን ያዘና አነሱንም ልክ እንደወረቀቱ እዛው ጥሎ ወጥቶ ሄደ፡፡
ከዛ ከእነሱ ስለሚጠበቀው ነገር፤ ስለዋና ዋና የግቢው ህግ፤ማድረግ ስለሚገባቸው መድረግ ስለሌለባቸው ነገር የአንድ ሰዓት ገለፃ ከተሰጣቸው በኃላ ናኦል ወደ ወንዶች ህንፃ ኑሀሚም ወደ ሴቶች ህንጻ ተወሰድና ከሌላ ከአንድ ሰው ጋር የሚጋሩት የራሳቸው መኝታ ቤት ተሰጣቸው፡፡በዚህ ሁኔታ አዲሱን ህይወታቸውን አህዱ ብለው ጀመሩ፡፡
ወደእዛ ግቢ ገብቶ በቃችሁ ውጡ ከመባሉ በፊት ለመውጣት መሞከር መጨረሻው ሞት ብቻ እንደሆነ ያወቁት ግቢውን በረገጡ በቀናቶች ውስጥ ነበር፡፡እንደተባለውም ስልጠናው የተለየ እና በእነሱ ዕድሜ ደረጃ ላለ ወጣት ይቅርና ለሙሉ ወጣትም የማይሞከር ነበር….ግን ስልጠናውን በቃኝ አልቻልኩም ማለት እራስን ለሞት አሳልፎ ከመስጠት ውጭ ሌላ የሚያሰገኘው ነገር የለም፡፡ስለዚህ የማይቻለን መቻል የግዳቸው ነበር፡፡ወታደራዊ ስልጠናው ብቻ ሳይሆን መደበኛ ትምህርቱ እራሱ በጣም ጥብቅ በሆነ ስነምግባር የሚሰጥ ነበር፡፡አንድ ልጅ እዛ ግቢ ሲገባ ሶስተኛ ክፍልም ይሁን ስድስታኛ ክፍል የ5 አመቱን የሥልጠና ጊዜ ጨርሷ ከዛ ጊቢ ተመርቆ ሲወጣ የ12ተኛ ክፍል ማትሪክ ወስዶ መሆን አለበት ፡፡በዛ የተነሳ በአመት ሁለት ክፍሎችን መማር የግድ ይላል፡፡ደግነቱ የትምህርት አሰጣጡ እጅግ ዘመናዊና ሁሉ ነገር የተሞላለት አስተማሪዎቹ ልክ እንደእነሱ በልዩ ችሎታቸውና ብቃታቸው የተመረጡ ጂኒዬሶችና ነገሮችን በቀላሉ በማስረዳት ችሎታቸው የተመሰከረላቸውና ስለሆኑ ጫናዎቹ የሚጠበቀውን ያህል እንዳይከብዳቸው ያግዛቸዋል፡፡በዛ ላይ እያንዳንዱ ሰልጣኝ እንደ ዝንባሌው በተለያዩ የስፖርት አይነቶቹ መሳተፍና የቋንቋ ስልጠናውም በተመሳሳይ ሁኔታ መውሰድ ይጠበቅበታል፡፡በተለይ ከውጭ ቋንቋ እንግሊዘኛና አረብኛ ሲማሩ ከሀገር ውስጥ እንደየ ምርጫቸው ከሚያውቁት በተጨማሪ ሁለት ቋንቋ እንዲማሩ ይደረጋል፡፡
ይሄ በሀገሪቱ የደህነነት መስሪያ ቤት በልዩ ፕሮጀክት እቅድ ተነድፎለት በጀት ተይዞለት እየተካሄደው ያለው ልዩ ስልጠና ለመጀመሪያው አንድ አመት ለሁሉም ተማሪዎች በጣም ከባድ አካልንም መንፈስንም በእኩል ደረጃ የሚያዝል ነበር፡፡ለዚህም ማሳያ በተቀመጠው ክራይቴሪያ ከተለያ ቦታ በተለያየ ዘዴ ተሰብስበው ከገቡ 80 ተማሪዎች መካከል በአመቱ መጨረሻ 17 ቱ መቋቋም አቅቶቸው ሞተው ነበረ፡፡ናኦልም እህቱ ከጎኑ ኖራ በየጊዜው ብርታት ባትሰጠው ኖሮ ከሞቾቹ መካከል መሰለፉ አይቀርም ነበር፡፡ለዚህ ነው መጀመሪያውኑ ሰልጣኞቹ ሲመለመሉ አስፈላጊው ክራይቴሪያ ዘመድና ጠያቂ የሌላቸው እንዲሆኑ የሚፈለገው፡፡
ኑሀሚ ግን ከሶስት ወር በላይ አልተቸገረችም ነበር….ካዛ በኃላ በየዲሲፕሊኑ ከፉክከሩ መድረክ ከፊት የምትሰለፍ፤ ለሁሉም ሰልጣኞች ምሳሌና ብርታት ሆና ነበረ የቀጠለችው፡፡አመስት አመቱ አልቆ ሲመረቁ ከአንድ ወንድ ጋር በእኩል ነጥብ አንደኛ በመሆን የወርቅ ዋናጫውን ተቀበለች፡፡ወንድሟ ናኦል 53 ተኛ ወጥቶ ተመረቀ፡፡እና 5 አመት ከኖሩበት ከእዛ ማሳልጠኛ ውስጥ ልክ እንደአገባባቸው በጨለማ መኪና ውስጥ ተሳፍረው እንዲወጡ ተደረገ.፡፡ከሰዕታት ጉዞ በኃላ ግን ልክ መስቀል አደባባይ አካባቢ መኪናዋ ቆማ ስታወርዳቸው የተቀበለቻቸው ምስራቅ ነበረች፡፡
በወቅቱ ሁለቱም ያለልዩነት ነበር የተጠመጠሙባት፡፡እሷም በደስታ እና በከፍተኛ እርካታ ነበር የተቀበለቻቸው፡፡ስታያቸው ከበፊቱ በጣም አድገው ሙሉ ወጣት ሆነው ስላየቻቸው እጅግ ተደስታ ነበር፡፡ከዛ መኪና ውስጥ አስገባቻቸውና ቀጥታ ወደወላጆቻቸው ቤት ነበር የወሰደቻቸው፡፡ከመኪና ስትወርድ አብረዋት ወረዱ…ሰፈሩን ሲያዩና የቆሙበትን ሲረዳ ሁለቱም ደንዝዘው ነበር..ቀጥታ ሁለቱንም መሀከላቸው ገባችና ግራና ቀኝ እጃቸውን ይዛ ወደ ግቢው በራፍ ይዛቸው ሄደች…ሁለቱም በዝምታና በድንዛዜ ተከተሏት..ካዛ አንኳኩታ ሰውዬው ሲወጣ የሆነ ነገር ትለዋለች ብለው ሲጠብቁ..ኪሶ ገባችና ቁልፍ በማውጣት..‹‹ይሄው ቃል በገባሁት መሰረት የወላጆቻችሁ ቤት ቁልፍ ››ብላ ኑሀሚ እጅ ላይ አስቀመጠችላት፡፡ኑሀሚ አላመነችም፡፡ በድንዛዛ እጇን አንቀሳቀሰችና ቁልፉን ከፈተች.. አሸከረከረች… ተከፈተ.. ተንደርድራ ወደውስጥ ገባች፡፡ ወንድሟም ተከተላት፡፡ በረንዳው ላይ እስኪደርሱ አልቆሙም…የሳሎኑን በራፍ ስትገፋው ተዘግቷል፡፡ እጆ ላይ ባለው ቁልፍ ሞከረች ፤ተከፈተ……፡፡ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ እነሱ ምንም ሳይለፉና ሳይጥሩ ነበር በምስራቅና በደህንነት መስሪያ ቤቱ ጥረት የወላጆቻቸው ቤት የተረከቡት፡፡
ከዛ ሁለት ወር ሰይቆይ ኑሀሚ በስልጠናዋ ባስመዘገበችው ብቃት ምክንያት ለተጨማሪ የሶስት አመት ስልጠና ወደ ራሺያ ተላከች፡፡
ናኦል ደግሞ ቤተሰቦቹ ቤት እየኖረ አዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ ገብቶ ትምህርቱን እየተማረ በተደራቢነት ከምስራቅ በሚሰጠው መመሪያና ተልዕኮ መሰረት የፊልድ ስረዎችን እንዲላመድ ተደረገ፡፡
ናኦል ከትዝታው ባኖ ግድግዳው ላይ የተለጠፈውን ሰዓት ሲያይ በጣም ነበር የተገረመው….ከለሊቱ10፡20 ሆኗል …ላለፉት አራት ሰዓት በላይ ባለፈ ታሪኩ ውስጥ ሰምጦ በትዝታ ሲዋልል ነበረ፡፡አካሉም ብቻ ሳይሆን አእምሮውም ዝሏ ነበር ፡፡
/////
ኮሎምቢያ/አሞዞን ደን ውስጥ
ካርሎስ ከጥልቅ እንቅልፉ ባነነ እና አይኖቹን ገለጠ፡፡በድቅድቁ ጨለማ በአማዞን ጥቅጥቅ ደን ውስጥ ግዙፍ ዛፍ ላይ ቆንጆና ወጣት ልጅ ደረቱ ላይ ተኝታ ነው ያገኘው…ያለበትን ሁኔታ አሰበና ፈገግ አለ፡፡ቀስ ብሎ ከደረቱ ላይ ቀና አድርጎ ሲያስነሳት ነበር ከገባችበት ጥልቅ ትዝታ የነቃችው፡፡
‹‹ወይ ሀሳቤን ጥዬ ተንፈላሰስኩብህ አይደል?››አለችው፡፡
‹‹አይ የተፈጥሮ ጥሪ አጨናንቆኝ ነው››
‹‹ማለት?››
‹‹ሽንቴን…ኩላሊቴ ልትፈነዳ ነው››
‹‹እ ..ነው..ወርደህ ልትሸና ነው?፡፡
‹‹አይ ምን አስወረደኝ..ብወርድ ሽንት ቤት የለ ..ሜዳ ላይ ነው የምሸናው፡፡ ማይደብርሽ ከሆነ እዚሁ ሆኜ ልለቀው ነው፡፡››
በጨለማ ውስጥ የማይታየውን ፈገግታዋን እየለገሰችው‹‹ምን ቸገረኝ..ልቀቀው.››አለችው
‹‹አመሰግናለው ››አለና ቆመ፡፡ ዚፕን መክፈት ሲጀመር.
‹‹እንዴ…››ብላ አጉረመረመች
‹‹ምነው?››
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ከምስራቅ ካር ስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ይገጥመናል ከሉት በላይ በጣም የተወሳሰበ ነገር ነበር የገጠማቸው፡፡በመጀመሪያ የት እንደተወሰዱ ያለማወቃቸው ነበር ከባድ ነገር፡፡ መስታወቱ ድፍን ጥቁር ሆኖ ወደውጭ በማያሳይ መኪና ውስጥ ተከተው…ለአንድ ሰዓት ለበለጠ ጊዜ ሲጓዙ ከቆ በኃላ መኪናዋ ቆመችና ሲወርዱ አምስት የሚሆኑ ባለአምስት ፎቅ ዘመናው ህንፃዎች ያሉበት የእግር ኳስ መጫወቻ ሜዳ፤ የመረብ ኳስ እና የመሳሰሉት ሜዳዎች ያሉበት ዙሪያውን በደን የተሸፈነ እና ቢያንስ 3 ሜትር ሚሆን ከኮንክሪትና ከብሎኬት የተሰራ አጥር ….በአጥሩ ጫፍ ላይ አደገኛ ሽቦ የተጠመጠመበት በጣም አስፈሪ ድባብ የተላበሰ ግዙፍ ስፍራ ነው፡፡በዛ ላይ .በተወሰነ ሜትር ርቀት በየሰዓቱ በሚቀያየሩ ቆፍጣና የጥበቃ ወታደሮች የሚታዩበት አስፈሪ ግቢ ውስጥ ነው ይዘዋቸው የገቡት፡፡
ይዞቸው ከመጡት መካከል አንድ ወደአንደኛው ፎቅ ይዟቸው ሄደና ወዳአንድ ቢሮ አስገባቸውና ምንነቱን ያለወቁት የሆነ ወረቀት አስፈርሞ በማስረከብ ቀሪውን ያዘና አነሱንም ልክ እንደወረቀቱ እዛው ጥሎ ወጥቶ ሄደ፡፡
ከዛ ከእነሱ ስለሚጠበቀው ነገር፤ ስለዋና ዋና የግቢው ህግ፤ማድረግ ስለሚገባቸው መድረግ ስለሌለባቸው ነገር የአንድ ሰዓት ገለፃ ከተሰጣቸው በኃላ ናኦል ወደ ወንዶች ህንፃ ኑሀሚም ወደ ሴቶች ህንጻ ተወሰድና ከሌላ ከአንድ ሰው ጋር የሚጋሩት የራሳቸው መኝታ ቤት ተሰጣቸው፡፡በዚህ ሁኔታ አዲሱን ህይወታቸውን አህዱ ብለው ጀመሩ፡፡
ወደእዛ ግቢ ገብቶ በቃችሁ ውጡ ከመባሉ በፊት ለመውጣት መሞከር መጨረሻው ሞት ብቻ እንደሆነ ያወቁት ግቢውን በረገጡ በቀናቶች ውስጥ ነበር፡፡እንደተባለውም ስልጠናው የተለየ እና በእነሱ ዕድሜ ደረጃ ላለ ወጣት ይቅርና ለሙሉ ወጣትም የማይሞከር ነበር….ግን ስልጠናውን በቃኝ አልቻልኩም ማለት እራስን ለሞት አሳልፎ ከመስጠት ውጭ ሌላ የሚያሰገኘው ነገር የለም፡፡ስለዚህ የማይቻለን መቻል የግዳቸው ነበር፡፡ወታደራዊ ስልጠናው ብቻ ሳይሆን መደበኛ ትምህርቱ እራሱ በጣም ጥብቅ በሆነ ስነምግባር የሚሰጥ ነበር፡፡አንድ ልጅ እዛ ግቢ ሲገባ ሶስተኛ ክፍልም ይሁን ስድስታኛ ክፍል የ5 አመቱን የሥልጠና ጊዜ ጨርሷ ከዛ ጊቢ ተመርቆ ሲወጣ የ12ተኛ ክፍል ማትሪክ ወስዶ መሆን አለበት ፡፡በዛ የተነሳ በአመት ሁለት ክፍሎችን መማር የግድ ይላል፡፡ደግነቱ የትምህርት አሰጣጡ እጅግ ዘመናዊና ሁሉ ነገር የተሞላለት አስተማሪዎቹ ልክ እንደእነሱ በልዩ ችሎታቸውና ብቃታቸው የተመረጡ ጂኒዬሶችና ነገሮችን በቀላሉ በማስረዳት ችሎታቸው የተመሰከረላቸውና ስለሆኑ ጫናዎቹ የሚጠበቀውን ያህል እንዳይከብዳቸው ያግዛቸዋል፡፡በዛ ላይ እያንዳንዱ ሰልጣኝ እንደ ዝንባሌው በተለያዩ የስፖርት አይነቶቹ መሳተፍና የቋንቋ ስልጠናውም በተመሳሳይ ሁኔታ መውሰድ ይጠበቅበታል፡፡በተለይ ከውጭ ቋንቋ እንግሊዘኛና አረብኛ ሲማሩ ከሀገር ውስጥ እንደየ ምርጫቸው ከሚያውቁት በተጨማሪ ሁለት ቋንቋ እንዲማሩ ይደረጋል፡፡
ይሄ በሀገሪቱ የደህነነት መስሪያ ቤት በልዩ ፕሮጀክት እቅድ ተነድፎለት በጀት ተይዞለት እየተካሄደው ያለው ልዩ ስልጠና ለመጀመሪያው አንድ አመት ለሁሉም ተማሪዎች በጣም ከባድ አካልንም መንፈስንም በእኩል ደረጃ የሚያዝል ነበር፡፡ለዚህም ማሳያ በተቀመጠው ክራይቴሪያ ከተለያ ቦታ በተለያየ ዘዴ ተሰብስበው ከገቡ 80 ተማሪዎች መካከል በአመቱ መጨረሻ 17 ቱ መቋቋም አቅቶቸው ሞተው ነበረ፡፡ናኦልም እህቱ ከጎኑ ኖራ በየጊዜው ብርታት ባትሰጠው ኖሮ ከሞቾቹ መካከል መሰለፉ አይቀርም ነበር፡፡ለዚህ ነው መጀመሪያውኑ ሰልጣኞቹ ሲመለመሉ አስፈላጊው ክራይቴሪያ ዘመድና ጠያቂ የሌላቸው እንዲሆኑ የሚፈለገው፡፡
ኑሀሚ ግን ከሶስት ወር በላይ አልተቸገረችም ነበር….ካዛ በኃላ በየዲሲፕሊኑ ከፉክከሩ መድረክ ከፊት የምትሰለፍ፤ ለሁሉም ሰልጣኞች ምሳሌና ብርታት ሆና ነበረ የቀጠለችው፡፡አመስት አመቱ አልቆ ሲመረቁ ከአንድ ወንድ ጋር በእኩል ነጥብ አንደኛ በመሆን የወርቅ ዋናጫውን ተቀበለች፡፡ወንድሟ ናኦል 53 ተኛ ወጥቶ ተመረቀ፡፡እና 5 አመት ከኖሩበት ከእዛ ማሳልጠኛ ውስጥ ልክ እንደአገባባቸው በጨለማ መኪና ውስጥ ተሳፍረው እንዲወጡ ተደረገ.፡፡ከሰዕታት ጉዞ በኃላ ግን ልክ መስቀል አደባባይ አካባቢ መኪናዋ ቆማ ስታወርዳቸው የተቀበለቻቸው ምስራቅ ነበረች፡፡
በወቅቱ ሁለቱም ያለልዩነት ነበር የተጠመጠሙባት፡፡እሷም በደስታ እና በከፍተኛ እርካታ ነበር የተቀበለቻቸው፡፡ስታያቸው ከበፊቱ በጣም አድገው ሙሉ ወጣት ሆነው ስላየቻቸው እጅግ ተደስታ ነበር፡፡ከዛ መኪና ውስጥ አስገባቻቸውና ቀጥታ ወደወላጆቻቸው ቤት ነበር የወሰደቻቸው፡፡ከመኪና ስትወርድ አብረዋት ወረዱ…ሰፈሩን ሲያዩና የቆሙበትን ሲረዳ ሁለቱም ደንዝዘው ነበር..ቀጥታ ሁለቱንም መሀከላቸው ገባችና ግራና ቀኝ እጃቸውን ይዛ ወደ ግቢው በራፍ ይዛቸው ሄደች…ሁለቱም በዝምታና በድንዛዜ ተከተሏት..ካዛ አንኳኩታ ሰውዬው ሲወጣ የሆነ ነገር ትለዋለች ብለው ሲጠብቁ..ኪሶ ገባችና ቁልፍ በማውጣት..‹‹ይሄው ቃል በገባሁት መሰረት የወላጆቻችሁ ቤት ቁልፍ ››ብላ ኑሀሚ እጅ ላይ አስቀመጠችላት፡፡ኑሀሚ አላመነችም፡፡ በድንዛዛ እጇን አንቀሳቀሰችና ቁልፉን ከፈተች.. አሸከረከረች… ተከፈተ.. ተንደርድራ ወደውስጥ ገባች፡፡ ወንድሟም ተከተላት፡፡ በረንዳው ላይ እስኪደርሱ አልቆሙም…የሳሎኑን በራፍ ስትገፋው ተዘግቷል፡፡ እጆ ላይ ባለው ቁልፍ ሞከረች ፤ተከፈተ……፡፡ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ እነሱ ምንም ሳይለፉና ሳይጥሩ ነበር በምስራቅና በደህንነት መስሪያ ቤቱ ጥረት የወላጆቻቸው ቤት የተረከቡት፡፡
ከዛ ሁለት ወር ሰይቆይ ኑሀሚ በስልጠናዋ ባስመዘገበችው ብቃት ምክንያት ለተጨማሪ የሶስት አመት ስልጠና ወደ ራሺያ ተላከች፡፡
ናኦል ደግሞ ቤተሰቦቹ ቤት እየኖረ አዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ ገብቶ ትምህርቱን እየተማረ በተደራቢነት ከምስራቅ በሚሰጠው መመሪያና ተልዕኮ መሰረት የፊልድ ስረዎችን እንዲላመድ ተደረገ፡፡
ናኦል ከትዝታው ባኖ ግድግዳው ላይ የተለጠፈውን ሰዓት ሲያይ በጣም ነበር የተገረመው….ከለሊቱ10፡20 ሆኗል …ላለፉት አራት ሰዓት በላይ ባለፈ ታሪኩ ውስጥ ሰምጦ በትዝታ ሲዋልል ነበረ፡፡አካሉም ብቻ ሳይሆን አእምሮውም ዝሏ ነበር ፡፡
/////
ኮሎምቢያ/አሞዞን ደን ውስጥ
ካርሎስ ከጥልቅ እንቅልፉ ባነነ እና አይኖቹን ገለጠ፡፡በድቅድቁ ጨለማ በአማዞን ጥቅጥቅ ደን ውስጥ ግዙፍ ዛፍ ላይ ቆንጆና ወጣት ልጅ ደረቱ ላይ ተኝታ ነው ያገኘው…ያለበትን ሁኔታ አሰበና ፈገግ አለ፡፡ቀስ ብሎ ከደረቱ ላይ ቀና አድርጎ ሲያስነሳት ነበር ከገባችበት ጥልቅ ትዝታ የነቃችው፡፡
‹‹ወይ ሀሳቤን ጥዬ ተንፈላሰስኩብህ አይደል?››አለችው፡፡
‹‹አይ የተፈጥሮ ጥሪ አጨናንቆኝ ነው››
‹‹ማለት?››
‹‹ሽንቴን…ኩላሊቴ ልትፈነዳ ነው››
‹‹እ ..ነው..ወርደህ ልትሸና ነው?፡፡
‹‹አይ ምን አስወረደኝ..ብወርድ ሽንት ቤት የለ ..ሜዳ ላይ ነው የምሸናው፡፡ ማይደብርሽ ከሆነ እዚሁ ሆኜ ልለቀው ነው፡፡››
በጨለማ ውስጥ የማይታየውን ፈገግታዋን እየለገሰችው‹‹ምን ቸገረኝ..ልቀቀው.››አለችው
‹‹አመሰግናለው ››አለና ቆመ፡፡ ዚፕን መክፈት ሲጀመር.
‹‹እንዴ…››ብላ አጉረመረመች
‹‹ምነው?››
👍63❤8
‹‹ቢያንስ ፊትህን ወደእዛ አዙር እንጂ››
==
በንጊት ጉዞዋ ያስደመሟት ሁለት ነገሮች ናቸው፡፡ አንደኛው የወፎቹ ዝማሬ ነው፡፡በየዛፎቹ ቅርንጫፎች መኖሪያቸውን የቀየሱት የተለያየ ዝርያ ያላቸው ወፎች… የተለያየ የዝማሬ ቅኝት ያለው ድምፅ ከዚህም ከዛም ሲለቁ ዋው ሙዚቃ ማለትስ ይሄ ነው እንድትል ነው ያሰኛት…በጣም የገረማት ደግሞ ብዛት ያላቸው ወፎች ብዛት ያለው የተለያየ አይነት ድምፅ
የሚያሰሙ ቢሆንም እሷ ጆሮ ሲደርስ ግን ፍፅም ስምም ፍፅም ህብር ፈጥሮ ነበር የሚሰማት፡፡ልክ የአንዷ ወፍ ድምፅ ጊታር..የሌላዋ የዋሽንት..የሌላዋ የክራር…የዛችኛዋ ደግሞ የፒያኖ .. እንደሆነ አይነት፡፡አዎ ሁሉም በተለያየ የሙዚቃ መሳሪያ አንድ አይነት መንፈሳዊ ህብረዝማሬ እንደሚዘምሩ አይነት ነው፡፡
ካርሎስ እንደነገራት ከሆነ አማዞን በእንስሳት ክምችቱ የአለም ግዙፉ መጋዘን ነው፡፡ከነዛ እንስሳት መካከል ደግሞ ወፎችም ይገኙበታል፡፡በአለማችን አስር ሺ ያህል የወፍ ዝርያዎች ሲኖሩ ከነዛ መካከል 3000 የሚሆኑት በዚሁ አሁን እሷ በምትገኝበት በአማዞን ደን ውስጥ የሚገኙ መሆናቸው አስደማሚ ነው፡፡እሷም እንደምታውቀው የገዛ ሀገሮ በእነዚህ የወፍ ዝርያዎች ክምችት ከአለም ቀላል ድርሻ የላትም…850 የሚሆኑ የወፍ ዝርያዎች በሀገረ ኢትዬጵያ እንደሚገኙ ማወቅ ልብን ያሞቃል
በዚ የለሊት ጉዞዋ በሁለተኛ ደረጃ የስደመማት ደግሞ ንጊቱ ቀርቦ ጭለማው ገፎ ፀሀዬ ስትወጣ ያለው እይታ ነው፡፡…. እሷ ከዛ በፊት በእኩለሊት ሰማይ ላይ አይኖቾን ሰቅላ ጨረቃን በማየት በውበቷ መፍዘዝና ከእሷ ጋር ማውራት ነበር ልምዷ፡፡በተለይ ከ15 ዓመታ በፊት እዛ በረንዳ ላይ ከወንድሟ ጋር በምትኖርበት ጊዜ ለሌት ላይ አንዳንዴ እንቅልፏ እንቢ ሲላት የለበሰችውን አሮጌ ብርድልብስና ከላይ የተደረበውን ጆንያ ስትገልጥ ቀጥታ የምታዬው ኮርኒስ ወይም ቆርቆሮ ሳይሆን ሰማዩን ነበር፡፡ሳማዩ ላይ ደግሞ ጨረቃዋ አንዳንዴ ሞልታ አንዳንዴ በግማሽ ትታይ ነበር፡፡እሷ ዙሪያ ደግሞ የተለያ ቅርፅና አቀማመጥ ያላቸው ለቁጥር የሚያታክቱ ኮከቦች፡፡ከኮከቦቹ መካከል ጎላ ጎላ ብለው አንድ ላይ ተጣብቀው የሚንቀሳቀሱ ስታይ እናትና አባቷ ይመስሎትና ከእይታዋ እስኪሰወሩ በስስትና በናፍቆት ታያቸው ነበር፡፡አዎ የእሷ ልምድ ያ ነው…የጨረቃንና የከዋክብቱን ብሩህናትና ውበት በጨለማ ማድነቅ፡፡
ፀሀይ ግን በአዲስ አበባ ስትወጣ ወጣች ነው…ስትገባ ደግሞ ገባች ነው፡፡ልብ ብላ አስተውላትም አታውቅም፡፡ፀሀይን ከሙቀቷና ከቃጠሎዋ ጋር እንጂ ከውበት ጋር በፍፅም የማየት እድሉ ገጥሟት አያውቅም፡፡ምን አልባት በወቅቱ የራበው ሆድ ውበትን ለማድነቅ ከባድ ሆኖባት ሊሆን ይችላል፡፡አሁን ግን ፊት ለፊት ካለው ተራራ እንደብርሀን አምድ ክብ ሰርታና ሚንቀለቀል እሳት መስላ እየተሸኮረመመች ብቅ ስትል ስታያት በረሽ ሄደሽ እቀፊያት የሚል ስሜት ነው የተፈታተናት፡፡ደግሞ ነፀብራቋ እዛ ደን ውስጥ እየተጠማዘዘ፤ እየተዘረጋና እየተሰበሰበ ልክ እንደአናኮናዳ በጉዞው አክሮባት የሚሰራው የአማዞን ወንዝ እና ሀይቅ መሰል የተለያዩ የውሀ አካላት ላይ አርፎ መልሶ ነፀብራቁን ሲረጭ ያለችበትን ቦታና ሁኔታ ነው ያስረሳት፡፡
ከካርሎስ እንደተረዳችው ከሆነ በአማዞን ደን ከ390 ቢሊዮን በላይ ዛፎች ይገኛሉ፡፡በአማዞን ደን ውስጥ እንደ ክረምት ፣ በጋ ፣ መኸር እና ፀደይ ያሉ ወቅቶች የሉም ፡፡ አነዚህ ጥቅጥቅ ደኖች አመቱን ሙሉ በዝናባማ ወቅቶች የተሸፈኑ ናቸው፡፡ይሄንን እራሷም አረጋግጣለች፡፡ይሄው በዚህ ደን ውስጥ መጓዝ ከጀመረችበት ቀን ጀምሮ የቀኑን አብዛኛውን ሰዓት በጀርበው አህያ የማይችለው የሚባል አይነት ዝናብ ስለሚንዠቀዘቅ ብረት እንደሚያነሳ ስፖርተኛ ደረቷ እየሰፋ ሁሉ እየመሰላት ነው….አማዞን ከ90 እስከ 140 ቢሊዮን ሜትሪክ ቶን ካርቦን በውስጡ በመያዝ የአለምን የካርቦን ልቀት ይቆጣጠራል፡፡የአለማችን 20 በመቶ ኦክስጅን የሚመረተውም በዚሁ እሷ በምትገኝበት በአማዞን ደን መሆኑን እና በዚህም ምክንያት “የፕላኔታችን ሳንባ ”ብለው እንደሚጠሩት አስረድቷታል፡፡
አዲስ አበባ /ኢትዬጵያ
ምስራቅ ለናኦል ከአምስት ቀን በኃላ ደወለችለት፡፡
‹‹ሄሎ ምስራቅ፡፡››
‹‹ሄሎ ጎረምሳው..ዝግጅትህን አጠናቀቅክ?››
‹‹አዎ ለጉብኝት አልሄድ ምን ዝግጅት ያስፈልጋል ብለሽ ነው..?ይልቅ አንቺ እንዴት ነው አለቀለሽ?››
‹‹አዎ …አሁን ሁሉን ነገር መቶ ፐርሰንት ጨርሼ በእጄ እንዳስገባው ነው የደወልኩልህ፡፡››
‹‹እንደው ምን ላድርግሽ?››
‹‹አጠገብህ ብሆን ጉንጮቼን ትሰመኝ ነበር?››ጠየቀችው፡፡
‹‹‹በትክክል..ግን ለምን ያለሽበት ድረስ መጥቼ እራት ምናምን ጋብዤሽ አላመሰግንሽም…በዛውም ሰነዶችን ወስዳለው፡፡››
‹‹አይ አያስፈልግም..ይልቅ ነገ ማታ ሁለት ሰዓት ላይ ቦሌ አየር ማረፊያ እንገናኝ… እሸኝሀለው…ሰነዶቹንም በዛን ጊዜ አስረክብሀለው፡፡››ብላ ያልጠበቀውን የምስራች አበሰረችው፡፡
‹‹ነገ …?እርግጠኛ ነሽ?››
‹‹አዎ… ምነው አይመችህም እንዴ?››
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ..ነገሮች ሁሉ ካሰብኩበት ጊዜ ቀድመው ሲከሰቱ ስለተመለከትኩ ተደምሜ ነው፡፡››
‹‹በል ..ነገ ሁለት ሰዓት..ቸው››ብላ ስልኩን ዘጋች፡፡ናኦል ይህቺን ሴት ይወዳታል…መውደድ ብቻ ሳይሆን ከምሩ ያፈቅራታል፡፡በህይወቱ ከምስረቅ ውጭ ሌላ ሴት አፍቅሮ አያውቅም፡፡.(እርግጥ ወሲባዊ ስሜቱን ለማርካት ሲል ከብዙ ሴቶች ጋር ወጥቷል)ግን ከእሷ ውጭ ያፈቀራት ሌላ ሴት የለችም…በእድሜ የእጥፍ ያህል ብትበልጠውም ድሮም ልጅ ሆኖም ሆነ አሁን ያፈቅራታል፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
==
በንጊት ጉዞዋ ያስደመሟት ሁለት ነገሮች ናቸው፡፡ አንደኛው የወፎቹ ዝማሬ ነው፡፡በየዛፎቹ ቅርንጫፎች መኖሪያቸውን የቀየሱት የተለያየ ዝርያ ያላቸው ወፎች… የተለያየ የዝማሬ ቅኝት ያለው ድምፅ ከዚህም ከዛም ሲለቁ ዋው ሙዚቃ ማለትስ ይሄ ነው እንድትል ነው ያሰኛት…በጣም የገረማት ደግሞ ብዛት ያላቸው ወፎች ብዛት ያለው የተለያየ አይነት ድምፅ
የሚያሰሙ ቢሆንም እሷ ጆሮ ሲደርስ ግን ፍፅም ስምም ፍፅም ህብር ፈጥሮ ነበር የሚሰማት፡፡ልክ የአንዷ ወፍ ድምፅ ጊታር..የሌላዋ የዋሽንት..የሌላዋ የክራር…የዛችኛዋ ደግሞ የፒያኖ .. እንደሆነ አይነት፡፡አዎ ሁሉም በተለያየ የሙዚቃ መሳሪያ አንድ አይነት መንፈሳዊ ህብረዝማሬ እንደሚዘምሩ አይነት ነው፡፡
ካርሎስ እንደነገራት ከሆነ አማዞን በእንስሳት ክምችቱ የአለም ግዙፉ መጋዘን ነው፡፡ከነዛ እንስሳት መካከል ደግሞ ወፎችም ይገኙበታል፡፡በአለማችን አስር ሺ ያህል የወፍ ዝርያዎች ሲኖሩ ከነዛ መካከል 3000 የሚሆኑት በዚሁ አሁን እሷ በምትገኝበት በአማዞን ደን ውስጥ የሚገኙ መሆናቸው አስደማሚ ነው፡፡እሷም እንደምታውቀው የገዛ ሀገሮ በእነዚህ የወፍ ዝርያዎች ክምችት ከአለም ቀላል ድርሻ የላትም…850 የሚሆኑ የወፍ ዝርያዎች በሀገረ ኢትዬጵያ እንደሚገኙ ማወቅ ልብን ያሞቃል
በዚ የለሊት ጉዞዋ በሁለተኛ ደረጃ የስደመማት ደግሞ ንጊቱ ቀርቦ ጭለማው ገፎ ፀሀዬ ስትወጣ ያለው እይታ ነው፡፡…. እሷ ከዛ በፊት በእኩለሊት ሰማይ ላይ አይኖቾን ሰቅላ ጨረቃን በማየት በውበቷ መፍዘዝና ከእሷ ጋር ማውራት ነበር ልምዷ፡፡በተለይ ከ15 ዓመታ በፊት እዛ በረንዳ ላይ ከወንድሟ ጋር በምትኖርበት ጊዜ ለሌት ላይ አንዳንዴ እንቅልፏ እንቢ ሲላት የለበሰችውን አሮጌ ብርድልብስና ከላይ የተደረበውን ጆንያ ስትገልጥ ቀጥታ የምታዬው ኮርኒስ ወይም ቆርቆሮ ሳይሆን ሰማዩን ነበር፡፡ሳማዩ ላይ ደግሞ ጨረቃዋ አንዳንዴ ሞልታ አንዳንዴ በግማሽ ትታይ ነበር፡፡እሷ ዙሪያ ደግሞ የተለያ ቅርፅና አቀማመጥ ያላቸው ለቁጥር የሚያታክቱ ኮከቦች፡፡ከኮከቦቹ መካከል ጎላ ጎላ ብለው አንድ ላይ ተጣብቀው የሚንቀሳቀሱ ስታይ እናትና አባቷ ይመስሎትና ከእይታዋ እስኪሰወሩ በስስትና በናፍቆት ታያቸው ነበር፡፡አዎ የእሷ ልምድ ያ ነው…የጨረቃንና የከዋክብቱን ብሩህናትና ውበት በጨለማ ማድነቅ፡፡
ፀሀይ ግን በአዲስ አበባ ስትወጣ ወጣች ነው…ስትገባ ደግሞ ገባች ነው፡፡ልብ ብላ አስተውላትም አታውቅም፡፡ፀሀይን ከሙቀቷና ከቃጠሎዋ ጋር እንጂ ከውበት ጋር በፍፅም የማየት እድሉ ገጥሟት አያውቅም፡፡ምን አልባት በወቅቱ የራበው ሆድ ውበትን ለማድነቅ ከባድ ሆኖባት ሊሆን ይችላል፡፡አሁን ግን ፊት ለፊት ካለው ተራራ እንደብርሀን አምድ ክብ ሰርታና ሚንቀለቀል እሳት መስላ እየተሸኮረመመች ብቅ ስትል ስታያት በረሽ ሄደሽ እቀፊያት የሚል ስሜት ነው የተፈታተናት፡፡ደግሞ ነፀብራቋ እዛ ደን ውስጥ እየተጠማዘዘ፤ እየተዘረጋና እየተሰበሰበ ልክ እንደአናኮናዳ በጉዞው አክሮባት የሚሰራው የአማዞን ወንዝ እና ሀይቅ መሰል የተለያዩ የውሀ አካላት ላይ አርፎ መልሶ ነፀብራቁን ሲረጭ ያለችበትን ቦታና ሁኔታ ነው ያስረሳት፡፡
ከካርሎስ እንደተረዳችው ከሆነ በአማዞን ደን ከ390 ቢሊዮን በላይ ዛፎች ይገኛሉ፡፡በአማዞን ደን ውስጥ እንደ ክረምት ፣ በጋ ፣ መኸር እና ፀደይ ያሉ ወቅቶች የሉም ፡፡ አነዚህ ጥቅጥቅ ደኖች አመቱን ሙሉ በዝናባማ ወቅቶች የተሸፈኑ ናቸው፡፡ይሄንን እራሷም አረጋግጣለች፡፡ይሄው በዚህ ደን ውስጥ መጓዝ ከጀመረችበት ቀን ጀምሮ የቀኑን አብዛኛውን ሰዓት በጀርበው አህያ የማይችለው የሚባል አይነት ዝናብ ስለሚንዠቀዘቅ ብረት እንደሚያነሳ ስፖርተኛ ደረቷ እየሰፋ ሁሉ እየመሰላት ነው….አማዞን ከ90 እስከ 140 ቢሊዮን ሜትሪክ ቶን ካርቦን በውስጡ በመያዝ የአለምን የካርቦን ልቀት ይቆጣጠራል፡፡የአለማችን 20 በመቶ ኦክስጅን የሚመረተውም በዚሁ እሷ በምትገኝበት በአማዞን ደን መሆኑን እና በዚህም ምክንያት “የፕላኔታችን ሳንባ ”ብለው እንደሚጠሩት አስረድቷታል፡፡
አዲስ አበባ /ኢትዬጵያ
ምስራቅ ለናኦል ከአምስት ቀን በኃላ ደወለችለት፡፡
‹‹ሄሎ ምስራቅ፡፡››
‹‹ሄሎ ጎረምሳው..ዝግጅትህን አጠናቀቅክ?››
‹‹አዎ ለጉብኝት አልሄድ ምን ዝግጅት ያስፈልጋል ብለሽ ነው..?ይልቅ አንቺ እንዴት ነው አለቀለሽ?››
‹‹አዎ …አሁን ሁሉን ነገር መቶ ፐርሰንት ጨርሼ በእጄ እንዳስገባው ነው የደወልኩልህ፡፡››
‹‹እንደው ምን ላድርግሽ?››
‹‹አጠገብህ ብሆን ጉንጮቼን ትሰመኝ ነበር?››ጠየቀችው፡፡
‹‹‹በትክክል..ግን ለምን ያለሽበት ድረስ መጥቼ እራት ምናምን ጋብዤሽ አላመሰግንሽም…በዛውም ሰነዶችን ወስዳለው፡፡››
‹‹አይ አያስፈልግም..ይልቅ ነገ ማታ ሁለት ሰዓት ላይ ቦሌ አየር ማረፊያ እንገናኝ… እሸኝሀለው…ሰነዶቹንም በዛን ጊዜ አስረክብሀለው፡፡››ብላ ያልጠበቀውን የምስራች አበሰረችው፡፡
‹‹ነገ …?እርግጠኛ ነሽ?››
‹‹አዎ… ምነው አይመችህም እንዴ?››
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ..ነገሮች ሁሉ ካሰብኩበት ጊዜ ቀድመው ሲከሰቱ ስለተመለከትኩ ተደምሜ ነው፡፡››
‹‹በል ..ነገ ሁለት ሰዓት..ቸው››ብላ ስልኩን ዘጋች፡፡ናኦል ይህቺን ሴት ይወዳታል…መውደድ ብቻ ሳይሆን ከምሩ ያፈቅራታል፡፡በህይወቱ ከምስረቅ ውጭ ሌላ ሴት አፍቅሮ አያውቅም፡፡.(እርግጥ ወሲባዊ ስሜቱን ለማርካት ሲል ከብዙ ሴቶች ጋር ወጥቷል)ግን ከእሷ ውጭ ያፈቀራት ሌላ ሴት የለችም…በእድሜ የእጥፍ ያህል ብትበልጠውም ድሮም ልጅ ሆኖም ሆነ አሁን ያፈቅራታል፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍67❤18👏6🔥3🥰3
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ብራዚልና ኮሎምቢያ ድንበር/አማዞን ደን ውስጥ
‹‹ካርሎስ››
‹‹አቤት››
‹‹ሀገሬ ኢትዬጵያ አባ..ይን ጨምሮ የብዙ ወንዞች ባለቤት ነች..ማለት የፈለኩት ብዙ ወንዞችን አይቼ አውቃለው…እና አማዞን እጅግ ገራሚ ከሆኑ ጥቂጥ ተፈጥሮዎች መካከል አንዱ ሆኖ ነው ያገኘሁት››
‹‹ምኑ ነው ያስገረመሽ?››
‹‹አማዞን አንዴ ወንዝ ይመስላል….አንዴ ደግሞ ሀይቅ ይሆናል ፣አሁን ተሸገርኩት ብለህ ለሳዕታት ከተጓዝክ በኃላ መልሶ ፊትህ ይጋረጣል››
‹‹ጥሩ ታዝበሻል፡፡አማዞን እና ገባር ወንዞቹ በአጠቃላይ ከ25,000 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው የውስጥ የውሃ መስመሮች መገናኛ ዋና ደም ስር ነው።ይህ ወንዝ ከተለያዩ ሀይቆች ጋር በሚገናኙበት ጊዜ, የወንዙ ጥልቀት 100 ሜትር ይደርሳል፡፡በበጋ ወቅት አማዞን 11 ኪሎ ሜትር ስፋት ሲደርስ 110 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ቦታን ያካልላል፡፡ዝናብ ሲሆን ደግሞ ስፈቱና ጥልቀቱ በሶስት እጥፍ ይጨምራል፡፡ በዚህ ወቅት የወንዙ ውሃ እስከ 20 ሜትር ከፍ ብሎ ስፋቱ ደግሞ 350 ሺህ ካሬ ኪሎ ሜትር መሬት ይሸፍናል፡፡በአማዞን እና ገባር ወንዞቹ ውስጥ ወደ 3,000 የሚጠጉ የዓሣ ዝርያዎች አሉበት››
ስለአማዞን ጥልቅ የሆነ እውቀት እንዳለው አመነች፡፡ ርእሱን ቀይራ‹‹እንስሳቱ ግን አያሳዝኑም››ስትል ጠየቀችው
‹‹እንዴት ማለት?››
‹‹አንድ አንድን ሲበላ …ጠገብኩ እፎይ ብሎ አረፍ ሲል በሌላው ደግሞ ሲበላ…››
‹‹አዎ ሁሉም እንስሳት ሰውንም ጭምር… ሁለችንም ለመብላትም ለመበላትም ነው የተፈጠርነው…፡፡››
‹‹የሰው ልጅ ደግሞ ይበላል እንጂ ይበላል እንዴ?››
‹‹አዎ … ወይ ቀን ሲጥለው ወይ ደግሞ ቀነ ሲጥል ይበላል፡፡አሁን እኔና አንቺ እዚህ ደን ውስጥ ስንት ቀን ከአውሬ መበላት ተርፈናል…ቀን ቢጥለን መበላታችን ይቀር ነበር…ባለፈው ከጓደኞቼ አንዱ በአናኮንዳ ሲበላ አላየሽም?፡፡
‹‹ያ እኮ ተዲያ ከመቶ ሚሊዬን አንድ የሚያጋጥም ነው፡፡››
‹‹አዎ ..ይሄ የሆነው የሰው ልጅ የሚያስብ እንስሳት በመሆኑ እራሱን ከዚህ አደጋ ለመጠበቅ ምን ማድረግ እንዳለበት እያሰበ እያሰበ መጣና እራሱን ከእንስሳ መኖሪያ እያራቀ መንደርና ከተማ እየሰራ ደህንነቱን ለማስጠበቅ ቻለ..እንደዛም ሆኖ ግን እድሜውን ማርዘም ቻለ እንጂ ሄዶ ሆዶ ከመበላት አይተርፍም….አሁን ስንቶቻችን ነን እርስ በርስ እየተባላላን ያለነው…?እኛ አሁን እዚህ ደን ውስጥ መከራችንን እያየን ያለነው ለምንድነው? በመሰል የሰው ልጆች ላለመበላት አይደል፡፡መበላት ሲባል የግድ ሰጋችንን ፈጭተው መዋጥ የለባቸውም …ከገደሉንና ከህይወት መስመር አንሸራተው ካስወጡን በሉን ማለት ነው፡፡››
‹‹ትክክል ነህ፡፡››
‹‹አዎ ትክክል ነኝ፡፡ ግን ደግሞ ሁሉም እንስሳት እኩል የመብላትና መበላት እጣ አላቸው ማለት አይደለም፡፡የጫካው ህግ የምግብ ስርዓት ልክ እንደፒራሚድ ነው፡፡ከፒራሚዱ የስረኛው ወለል ያሉ መበላት የየእለት ጭንቀታቸውና እጣቸው ነው፡፡የፒራሚዲ ጫፍ ያሉት ደግሞ እነአንበሳ ነብር የመሳሰሉትና ማለቴ ነው..ማደን መያዝና መዘንጠል የየእለት ስራቸውና ተግባራቸው ነው፡፡››
‹‹ተመስገን እኛ የሰው ልጅ እንደዚህ አለመሆናችን፡፡››
ፈገግ ብሎ ሳቀባት፡፡
‹‹ምነው ትክክል አይደለሁም እንዴ?››
አይ እንደውም ይሄንን ፒራሚዱን የምግብ ስርዓት ከእንስሳቱ ኮርጆ የራሱን ማሻሻያ አድርጎበት በጥበብ ነው እየተገበረ ያለው፡፡የአለም 90 ፐርሰንት ሀብት በ10 ፐርሰንት በሚሆኑ ቱጃሮች እጅ ነው ያለው ..ያ ማለት በሰው ልጅ ኪንግደም ውስጥ 10 ፐርሰንቱ የፒራሚዱ ጫፍ ላይ ያሉት ናቸው፡፡እነሱ የ90 ፐርሰንቱን ላብና ወዝ በተለያ ሚስጥራዊና ዘዴ ቅርጥፍ አድርጎ ይሰለቅጡታል፡፡››
አይን አይኗን በስስት እያያት‹‹ስለአንቺ ሳስብ ምን እንደሚገርመኝ ታውቂያለሽ?››አላት
የተወሰነ ጉጉት በሚታይበት የስሜት መነቃቃት‹‹እስኪ ምንድነው ንገረኝ ልስማው ››ስትል መለሰችት
‹‹ያንቺ ነፍስ ያንቺ ብቻ እንዳልሆነች ነው እንድረዳ ያደረግሺኝ..የነፍስሽ ክፍያ የወንድምሽ ንበረት ነው የሚመስለው፡፡አደራ አንቺ ጋር አስቀምጪልኝ ብሎ እንደሰጠሸና ያንን አደራሻን ላለመብላት የመጨረሻውን ጥረት እየጣርሽ እንደሆነ ነው፡፡ያ ነው እንዲህ ብርቱና ጠንካራ እንድትሆኚ ያደረገሽ….››
‹‹ጥሩ ገልፀሀዋል..ግን ይሄ የእኔ ብቻ ችግር አይመስለኝም፡፡የሰው ልጅ ሁሉ ለቤተሰቡ ይብዛም ይነስ እንጂ ተመሳሳይ አይነት እይታ አለው፡፡ማንም ቢሆን ነፍሱ የእሱ ብቻ አይደለም…እሱ ሲያመው የሚያማቸው እሱ ሲደሰት ደስ የሚላቸው ቤተሰቦች ይኖሩታል፡፡ለእነሱ ሲል እራሱን ከአደጋ ይጠብቃል..ለእነሱ ሲል ጠንክሮ ይሰራል፡፡አዎ ጠንካራ የቤተሰብ ትስስር ያለው ሰው ጠንካራ ስብዕና ይኖረዋል፡፡እነሱ በህይወት ጉዞ ትክክለኛውን መስመር መርቶ እንዲጓዝ ብርታትና ጥንካሬ ይሆኑታል፡፡.አብዛኛው ሰው የሚኖርላቸው የሚወዳቸውና የሚወዱት አምስት ወይም አስር ሰዎች ይሩታል፡፡እኔ የእኔ የምለው አንድ ወንድሜ ብቻ ስለሆነ ነው፡፡ያለኝን ፍቅር ጠቅላላ ተሰብስቦና ተከማችቶ አንድ ወንድሜ ላይ ስላረፈ ነው፡፡››
‹‹ገባኝ ..ጥሩ ገልፀሸዋል….ቀናሁበት››
‹‹ግድ የለህም አትቅና፡፡ ፍቅር ከመጠን ሲያልፍ ትንፋሽ ይነሳል…እንዲህ እንደምታስበው ጥሩ ጎን ብቻ አይደለም ያለው፡፡ወንድሜ የ10 ደቂቃ ታላቄ ወይም በሌላ አገላለፅ መንትያዬ ነው፡፡አንድ ማህፀን ውስጥ አንድ አይነት ሰዓት አንድ አይነት ምግብ እየተመገብን ነው የኖርነው…ከተወለድንም በኃላ እንደዛው… ቢሆንም በተለይ ወላጆቻችን ከሞቱ በኃላ ልክ እንደታናሽ ወንድሜ ነው የምቆጣጠረው፡፡የት ገባህ?የት ወጣህ….?በዚህ ግባ በዚህ ውጣ..አንዳንዴ ጭቅጭቄ ለእኔ ለራሴ ይሰለቸኛል..የሚገርመኝ እሱ ግን የእኔን ጭቅጭቅ የሚታገስበት የሚገርም ትእግስት አለው….ዝም ያልኩት ቀን እንደውም ምን ነካት ብሎ ይንቆራጠጣል….፡፡››
…
አዲስአበባ
///
ናኦል ከምስራቅ ጋር እንደተቃጠሩት በማግስቱ ምሽት 1፡30 ነበር ቦሌ የደረሰው፡፡
‹‹ለሁለት 10 ጉዳይ ሲል ልደውልላት ወይስ ሁለት ሰዓት ይሙላ?›› እያለ ከራሱ ጋር ሲሞገት ከፊት ለፊት ሽክ ያለ አለባበስ ለብሳ በአስፈሪ ግርማ ሞገሶ አንድ መለስተኛ ዘመናዊ ሻንጣ በእጇ በመጎተት እያሽከረከረች ወደእሱ ስትቀርብ ተመለከተ፡፡ፊቱ ሁሉ አንፀባረቀ፡፡
‹‹እሺ..ቀድመህ ነው የደረስከው››አለችው፡፡
‹‹አዎ መቅደምም ነበረብኝ…ግን ሻንጣው ለምን አስፈለገ …?የሚያስፈልጉኝን ነገሮች እንደማልይዝ ጠርጥረሽ ነው አይደል? ዝም ብለሽ ነው የሰጋሽው፡፡››አለ፡፡እሱ ..ሻንጣውን ለእሱ ብላ የሚያስፈልጉትን እቃዎች ይዛበት የመጣች ነው የመሰለው፡፡
‹‹አይ ጎረምሳው ተሳስተሀል..ይሄ ሻንጣ የእኔ ነው፡፡››
‹‹የእኔ ነው ማለት?››
‹‹የእኔ ነዋ …እኔም ተጓዥ ነኝ፡፡ይልቅ ና እንግባ፡፡›› አለችና ከፊቱ ቀደመች፡፡
‹‹ወደየት ልትሄጂ ነው.?በአንድ ቀን ሁለታችንም ከአገር እንደምንወጣ አላወቅም ነበር፡፡››
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ክፍል_አስራ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ብራዚልና ኮሎምቢያ ድንበር/አማዞን ደን ውስጥ
‹‹ካርሎስ››
‹‹አቤት››
‹‹ሀገሬ ኢትዬጵያ አባ..ይን ጨምሮ የብዙ ወንዞች ባለቤት ነች..ማለት የፈለኩት ብዙ ወንዞችን አይቼ አውቃለው…እና አማዞን እጅግ ገራሚ ከሆኑ ጥቂጥ ተፈጥሮዎች መካከል አንዱ ሆኖ ነው ያገኘሁት››
‹‹ምኑ ነው ያስገረመሽ?››
‹‹አማዞን አንዴ ወንዝ ይመስላል….አንዴ ደግሞ ሀይቅ ይሆናል ፣አሁን ተሸገርኩት ብለህ ለሳዕታት ከተጓዝክ በኃላ መልሶ ፊትህ ይጋረጣል››
‹‹ጥሩ ታዝበሻል፡፡አማዞን እና ገባር ወንዞቹ በአጠቃላይ ከ25,000 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው የውስጥ የውሃ መስመሮች መገናኛ ዋና ደም ስር ነው።ይህ ወንዝ ከተለያዩ ሀይቆች ጋር በሚገናኙበት ጊዜ, የወንዙ ጥልቀት 100 ሜትር ይደርሳል፡፡በበጋ ወቅት አማዞን 11 ኪሎ ሜትር ስፋት ሲደርስ 110 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ቦታን ያካልላል፡፡ዝናብ ሲሆን ደግሞ ስፈቱና ጥልቀቱ በሶስት እጥፍ ይጨምራል፡፡ በዚህ ወቅት የወንዙ ውሃ እስከ 20 ሜትር ከፍ ብሎ ስፋቱ ደግሞ 350 ሺህ ካሬ ኪሎ ሜትር መሬት ይሸፍናል፡፡በአማዞን እና ገባር ወንዞቹ ውስጥ ወደ 3,000 የሚጠጉ የዓሣ ዝርያዎች አሉበት››
ስለአማዞን ጥልቅ የሆነ እውቀት እንዳለው አመነች፡፡ ርእሱን ቀይራ‹‹እንስሳቱ ግን አያሳዝኑም››ስትል ጠየቀችው
‹‹እንዴት ማለት?››
‹‹አንድ አንድን ሲበላ …ጠገብኩ እፎይ ብሎ አረፍ ሲል በሌላው ደግሞ ሲበላ…››
‹‹አዎ ሁሉም እንስሳት ሰውንም ጭምር… ሁለችንም ለመብላትም ለመበላትም ነው የተፈጠርነው…፡፡››
‹‹የሰው ልጅ ደግሞ ይበላል እንጂ ይበላል እንዴ?››
‹‹አዎ … ወይ ቀን ሲጥለው ወይ ደግሞ ቀነ ሲጥል ይበላል፡፡አሁን እኔና አንቺ እዚህ ደን ውስጥ ስንት ቀን ከአውሬ መበላት ተርፈናል…ቀን ቢጥለን መበላታችን ይቀር ነበር…ባለፈው ከጓደኞቼ አንዱ በአናኮንዳ ሲበላ አላየሽም?፡፡
‹‹ያ እኮ ተዲያ ከመቶ ሚሊዬን አንድ የሚያጋጥም ነው፡፡››
‹‹አዎ ..ይሄ የሆነው የሰው ልጅ የሚያስብ እንስሳት በመሆኑ እራሱን ከዚህ አደጋ ለመጠበቅ ምን ማድረግ እንዳለበት እያሰበ እያሰበ መጣና እራሱን ከእንስሳ መኖሪያ እያራቀ መንደርና ከተማ እየሰራ ደህንነቱን ለማስጠበቅ ቻለ..እንደዛም ሆኖ ግን እድሜውን ማርዘም ቻለ እንጂ ሄዶ ሆዶ ከመበላት አይተርፍም….አሁን ስንቶቻችን ነን እርስ በርስ እየተባላላን ያለነው…?እኛ አሁን እዚህ ደን ውስጥ መከራችንን እያየን ያለነው ለምንድነው? በመሰል የሰው ልጆች ላለመበላት አይደል፡፡መበላት ሲባል የግድ ሰጋችንን ፈጭተው መዋጥ የለባቸውም …ከገደሉንና ከህይወት መስመር አንሸራተው ካስወጡን በሉን ማለት ነው፡፡››
‹‹ትክክል ነህ፡፡››
‹‹አዎ ትክክል ነኝ፡፡ ግን ደግሞ ሁሉም እንስሳት እኩል የመብላትና መበላት እጣ አላቸው ማለት አይደለም፡፡የጫካው ህግ የምግብ ስርዓት ልክ እንደፒራሚድ ነው፡፡ከፒራሚዱ የስረኛው ወለል ያሉ መበላት የየእለት ጭንቀታቸውና እጣቸው ነው፡፡የፒራሚዲ ጫፍ ያሉት ደግሞ እነአንበሳ ነብር የመሳሰሉትና ማለቴ ነው..ማደን መያዝና መዘንጠል የየእለት ስራቸውና ተግባራቸው ነው፡፡››
‹‹ተመስገን እኛ የሰው ልጅ እንደዚህ አለመሆናችን፡፡››
ፈገግ ብሎ ሳቀባት፡፡
‹‹ምነው ትክክል አይደለሁም እንዴ?››
አይ እንደውም ይሄንን ፒራሚዱን የምግብ ስርዓት ከእንስሳቱ ኮርጆ የራሱን ማሻሻያ አድርጎበት በጥበብ ነው እየተገበረ ያለው፡፡የአለም 90 ፐርሰንት ሀብት በ10 ፐርሰንት በሚሆኑ ቱጃሮች እጅ ነው ያለው ..ያ ማለት በሰው ልጅ ኪንግደም ውስጥ 10 ፐርሰንቱ የፒራሚዱ ጫፍ ላይ ያሉት ናቸው፡፡እነሱ የ90 ፐርሰንቱን ላብና ወዝ በተለያ ሚስጥራዊና ዘዴ ቅርጥፍ አድርጎ ይሰለቅጡታል፡፡››
አይን አይኗን በስስት እያያት‹‹ስለአንቺ ሳስብ ምን እንደሚገርመኝ ታውቂያለሽ?››አላት
የተወሰነ ጉጉት በሚታይበት የስሜት መነቃቃት‹‹እስኪ ምንድነው ንገረኝ ልስማው ››ስትል መለሰችት
‹‹ያንቺ ነፍስ ያንቺ ብቻ እንዳልሆነች ነው እንድረዳ ያደረግሺኝ..የነፍስሽ ክፍያ የወንድምሽ ንበረት ነው የሚመስለው፡፡አደራ አንቺ ጋር አስቀምጪልኝ ብሎ እንደሰጠሸና ያንን አደራሻን ላለመብላት የመጨረሻውን ጥረት እየጣርሽ እንደሆነ ነው፡፡ያ ነው እንዲህ ብርቱና ጠንካራ እንድትሆኚ ያደረገሽ….››
‹‹ጥሩ ገልፀሀዋል..ግን ይሄ የእኔ ብቻ ችግር አይመስለኝም፡፡የሰው ልጅ ሁሉ ለቤተሰቡ ይብዛም ይነስ እንጂ ተመሳሳይ አይነት እይታ አለው፡፡ማንም ቢሆን ነፍሱ የእሱ ብቻ አይደለም…እሱ ሲያመው የሚያማቸው እሱ ሲደሰት ደስ የሚላቸው ቤተሰቦች ይኖሩታል፡፡ለእነሱ ሲል እራሱን ከአደጋ ይጠብቃል..ለእነሱ ሲል ጠንክሮ ይሰራል፡፡አዎ ጠንካራ የቤተሰብ ትስስር ያለው ሰው ጠንካራ ስብዕና ይኖረዋል፡፡እነሱ በህይወት ጉዞ ትክክለኛውን መስመር መርቶ እንዲጓዝ ብርታትና ጥንካሬ ይሆኑታል፡፡.አብዛኛው ሰው የሚኖርላቸው የሚወዳቸውና የሚወዱት አምስት ወይም አስር ሰዎች ይሩታል፡፡እኔ የእኔ የምለው አንድ ወንድሜ ብቻ ስለሆነ ነው፡፡ያለኝን ፍቅር ጠቅላላ ተሰብስቦና ተከማችቶ አንድ ወንድሜ ላይ ስላረፈ ነው፡፡››
‹‹ገባኝ ..ጥሩ ገልፀሸዋል….ቀናሁበት››
‹‹ግድ የለህም አትቅና፡፡ ፍቅር ከመጠን ሲያልፍ ትንፋሽ ይነሳል…እንዲህ እንደምታስበው ጥሩ ጎን ብቻ አይደለም ያለው፡፡ወንድሜ የ10 ደቂቃ ታላቄ ወይም በሌላ አገላለፅ መንትያዬ ነው፡፡አንድ ማህፀን ውስጥ አንድ አይነት ሰዓት አንድ አይነት ምግብ እየተመገብን ነው የኖርነው…ከተወለድንም በኃላ እንደዛው… ቢሆንም በተለይ ወላጆቻችን ከሞቱ በኃላ ልክ እንደታናሽ ወንድሜ ነው የምቆጣጠረው፡፡የት ገባህ?የት ወጣህ….?በዚህ ግባ በዚህ ውጣ..አንዳንዴ ጭቅጭቄ ለእኔ ለራሴ ይሰለቸኛል..የሚገርመኝ እሱ ግን የእኔን ጭቅጭቅ የሚታገስበት የሚገርም ትእግስት አለው….ዝም ያልኩት ቀን እንደውም ምን ነካት ብሎ ይንቆራጠጣል….፡፡››
…
አዲስአበባ
///
ናኦል ከምስራቅ ጋር እንደተቃጠሩት በማግስቱ ምሽት 1፡30 ነበር ቦሌ የደረሰው፡፡
‹‹ለሁለት 10 ጉዳይ ሲል ልደውልላት ወይስ ሁለት ሰዓት ይሙላ?›› እያለ ከራሱ ጋር ሲሞገት ከፊት ለፊት ሽክ ያለ አለባበስ ለብሳ በአስፈሪ ግርማ ሞገሶ አንድ መለስተኛ ዘመናዊ ሻንጣ በእጇ በመጎተት እያሽከረከረች ወደእሱ ስትቀርብ ተመለከተ፡፡ፊቱ ሁሉ አንፀባረቀ፡፡
‹‹እሺ..ቀድመህ ነው የደረስከው››አለችው፡፡
‹‹አዎ መቅደምም ነበረብኝ…ግን ሻንጣው ለምን አስፈለገ …?የሚያስፈልጉኝን ነገሮች እንደማልይዝ ጠርጥረሽ ነው አይደል? ዝም ብለሽ ነው የሰጋሽው፡፡››አለ፡፡እሱ ..ሻንጣውን ለእሱ ብላ የሚያስፈልጉትን እቃዎች ይዛበት የመጣች ነው የመሰለው፡፡
‹‹አይ ጎረምሳው ተሳስተሀል..ይሄ ሻንጣ የእኔ ነው፡፡››
‹‹የእኔ ነው ማለት?››
‹‹የእኔ ነዋ …እኔም ተጓዥ ነኝ፡፡ይልቅ ና እንግባ፡፡›› አለችና ከፊቱ ቀደመች፡፡
‹‹ወደየት ልትሄጂ ነው.?በአንድ ቀን ሁለታችንም ከአገር እንደምንወጣ አላወቅም ነበር፡፡››
👍60❤6👏2🔥1🥰1
‹‹ይሄው አወቅክ አይደል..?ቆይ ስታስበው አንተን ብቻህን የምልክህ ይመስልሀል..?ለእኔም እኮ እህቴ ነች..አንተም ወንድሜ ነህ፡፡..እናንተን ለአደጋ ጥዬ ተረጋግቼ ህይወቴን መኖር አልችልም፡፡››
‹‹አና አብረሺኝ ነው የምትሄጂው?››
‹‹አዎ በትክክል፡፡››
ደስታው ሊያስከረው ደረሰ..በዕድሜው ረጅም ጊዜ ሲያደንቃት ..ሲሰማትና …ሲወዳት ከኖረው ሴት ጋር በሰማይ ሰንጥቆ አህጉራቱን አቆርጦ ውቅያኖስን ቁልቁል እያየ ሲጓዝ አሰበና ደስ አለው…አይ የሰው ልጅ እጅግ መራር ሀዘን ውስጥ ባለበት ጊዜ ውስጥ ሳይቀር የሆነ ለደቂቃም ቢሆን ፈገግ የሚያስብለው ነገር ማግኘቱ አይቀርም ..ያቺ የፈገግታ ብልጭታ ደግሞ ከትልቁ ሀዘን አግራሞት እንዲወጣ ብርታት ትሆነዋለች፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹አና አብረሺኝ ነው የምትሄጂው?››
‹‹አዎ በትክክል፡፡››
ደስታው ሊያስከረው ደረሰ..በዕድሜው ረጅም ጊዜ ሲያደንቃት ..ሲሰማትና …ሲወዳት ከኖረው ሴት ጋር በሰማይ ሰንጥቆ አህጉራቱን አቆርጦ ውቅያኖስን ቁልቁል እያየ ሲጓዝ አሰበና ደስ አለው…አይ የሰው ልጅ እጅግ መራር ሀዘን ውስጥ ባለበት ጊዜ ውስጥ ሳይቀር የሆነ ለደቂቃም ቢሆን ፈገግ የሚያስብለው ነገር ማግኘቱ አይቀርም ..ያቺ የፈገግታ ብልጭታ ደግሞ ከትልቁ ሀዘን አግራሞት እንዲወጣ ብርታት ትሆነዋለች፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍65❤14👎3🥰3👏3
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ብራዚል/ፔሩ
ናኦል እና ምስራቅ የወደቧ ውብ ከተማ ሪዬ ዲጄኔሮ እንደደረሱ ቀጥታ ታክሲ ይዘው ወደ ሆቴል ነው ያመሩት፡፡ለሁለትም እንዲህ አይነት ረጅም የአየር ላይ ጉዞ ሲጓዙ የመጀመሪያቸው ስለሆነ ድካሙ ከልክ ያለፈ ነበር..በተለይ ናኦል ከሀገር ውስጥ በረራዎች በስተቀር ድንበር ሲሻገር እራሱ የመጀመሪያው ገጠመኙ ሰለሆነ ጉዞ እንደህልም ነው የሆነበት ፡፡ሁለቱ ከአየር መንገድ ወጥተው ታክሲ ተሳፍረው ወደሆቴል እየሄዱ እያሉ ከሻንጣዋ የጎን ኪስ አንድ ወረቀት አወጣችና አቀበለችው፡፡
ተቀብሎ እያያት‹‹ምንድነው?፡፡››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አንብበው፡፡››
የተጣጠፈውን ወረቀት ገለጠና አየው..ከወረቀቱ ጫፍ በግራ በኩል የእሱ ፎቶ ተለጥፎበታል፡፡ በተመሳሳይ መስመር በቀኝ በኩል ደግሞ የራሷ የምስራቅ ፎቶ አለበት፡፡በመደነቅ እንደተሞላ ማንበብ ጀመረ‹‹ሁለቱ ባልና ሚስት እንደሆኑ የሚያወራና ያንንም የሚያረጋግጥ ህጋዊ የጋብቻ ሰርተፍኬት ነው፡፡ባለማመን አይኑን ጨፈን ገለጥ ጨፈን ገለጥ በማድረግ ደጋግሞ አየው፡፡ትክክል ነው፡፡
‹‹ውይ እኔ እኮ በጣም እድለኛ ሰው ነኝ ..መቼ ነው ህልሜ እንዲህ ያሳከሁት?መቼ ነው በአለም ላይ እጅግ የማደንቃትንና የምወዳትን የህልሜን ሴት ያገባሁት….?እስኪ ንገሪኝ መቼ ነው ?››
‹‹ጎረምሳው አረጋጋው..ይሄ ኑሀሚን በመፈለግ ሂደት በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ስለሆነ ነው፡፡ይሄንን ተልዕኮችን እስኪጠናቀቅ እኔና አንተ ባልና ሚስት ነን፡፡የተጋባንበትን ቀን በቃልህ ሸምድደው..ሁለት ወር ሆኖናል፡፡ገና ትኩስ ባለትዳሮች ነን፡፡እንኳ…ደግሞ ቀለበትን በትከክለኛ እጣትህ ላይ አጥልቀው›› አለችናን እጇ ላይ ካለው ሁለት ቀለበት መካከል አንድን አቀበለችው፤ ሁለተኛውን እራሷ ጣት ላይ አጠለቀች፡፡ተቀበላትና በሚፍለቀለቅ ፈገግታው ታጅቦ ቀለበቱን አጠለቀው፡፡
‹‹…ይሄው..አሁን ሁሉ ነገር ውብና ፍፅም ትክክል ሆኗል…ግን ይሄንን ሰርተፍኬት እኔ ጋር ቢሆን ምን ይመስልሻል?››
‹‹ግድ የለም ያዘው ..የረሴ ድርሻ አለኝ..››አለችው በፈገግታ፡፡
ከዛ ሆቴል ደርሰው በባልና ሚስት ተመዝግበው አንድ አልጋ ያለው መኝታ ክፍል ያዙ፡፡ከምስራቅ ጋር በጣም በርካታ ቀናቶች ተመሳሳይ ቤት ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ክፍሎችና የተለያዩ አልጋዎች ላይ የመተኛት አጋጣሚ ቢኖራቸውም እንዲህ አንድ አልጋ ላይ የመተኛት እድል አጋጥሞት አያውቅም….አሁን ያ እድል እውን ሊሆንለት እንደሆነ ሲያስብ ልቡ በውስጡ መፈንጠዝ ጀመረች፡፡
///
በማግስቱ ከብራዚል ወደፔሩዋ ከተማ ሊማ ተጓዙና ምንም ሳያርፍ ቀጥታ ወደኢኩዬቶስ በረሩ…እንደደረሱ ለኡበሩ ሹፌር የተነገራቸውን ሆቴል ስም ነገሩና ወደዛው ወሰዳቸው፡፡ልክ ከኡበሩ የየራሳውን ሻንጣ ይዘው ወረዱና ወደሆቴል መጓዝ ሲጀምሩ‹‹እንግዲህ ከእስከአሁኑ በላይ በጣም ጠንቃቃ ሁኑ ..ከዚህ ሰዓት ጀምሮ በእርግጠኝነት በእነሱ ሰዎች እይታ ስር ነው ያለነው…ሆቴሉ ውስጥም ሆነ የምንገባበት መኝታ ቤት ውስጥ ካሜራ እንደሚያስቀምጡ እርግጠኛ ነኝ፡፡››አለችው፡፡
‹‹ገባኝ..እጠነቀቃለሁ፡፡››
‹‹ሆቴል ብክ አደረጉና ፅዱ የሆነ ባለአንድ አልጋ መኝታ ቤት ተሰጣቸው፡፡ገብተው ዕቃቸውን አመቻችተው እንዳስቀመጡ..‹‹የእኔ ፍቅር ትንሽ ሞቆኛል ሻወር ልወስድ ነው..አስከዛው ጋደም ብለህ ጠብቀኝ ..››አለችና እዛው እያያት ልብሷን በማወላለቅ እርቃኗን ሰውነቷ ላይ በቀረ ሰማያዊ ፓንት ብቻ ወደ ሻወር ቤት ሄደች፡፡እሱም በፍዘት ሲያያት ቆይቶ ሻወር ቤት ገብታ እስክትሰወርበት እየተመለከታት ነበር.፡፡ሌላ ቀን እዛ ሀገራቸው ምድር ላይ ሆኖ እንደዚህ ፊት ለፊቱ ልብሷን አወላልቃ እንዲህ እርቃኗን ቆማ አይቷት ቢሆን ኖሮ ወይ ተንደርድሮ ሄዶ ይጠመጠምባታል..ወይ ደግሞ እራሱን ስቶ መሬት ይዘረር ነበር፡፡አሁን ግን ከደቂቃዎች በፊት ያስጠነቀቀችውን እያሰበ እራሱን በትልቅ ጥረት ተቆጣጥሮ በትግስት ባለበት መርጋት ቻለ..፡፡
እሷ እየሰራች ያለውን ድራማ ይበልጥ ሊያደምቀው ወሰነና ልክ እሷ እንዳደረገችው ልብሱን አወላለቀ እና በፓንቱ ብቻ ወደሻወር ቤት ሄደና ገርበብ ያለውን በራፍ ገፋ በማድረግ ወደውስጥ ገባ ፡፡አልጠበቀችም ነበርና ስታየው ደነገጠች፡፡ሰውነቷን ስታሽበት የነበረው ሳሙና ከእጇ ተንሸራተተና ወደወለሉ ወደቀባት፡፡
‹‹የእኔ ፍቅር ላሽሽ እኮ ነው የመጣሁት…››አለና ሳሙናውን ጎንበስ ብሎ በማንሳት ሰውነቷን በአራፋው ያዳርስ ጀመር፡፡እሱ ብቻ ሳይሆን እሷም እጆቹ ሰውነቷ ላይ ሲሽከረከሩ ድንዝዝ እያለች ነው፡፡ልትቆጣጠረው የማትችል ስሜት በውስጧ ሲንተከተክና ልቧን ድክምክም ሲያደርጋት እየታወቃት ነው፡፡በዚህ ስሜት ተሸንፋ ዝልፍልፍ ብላ ክንዱ ላይ ከመውደቋ እና ባሳደገችው ልጅ ፊት ከመዋረዷ በፊት የሆነ ነገር ማድረግ እንዳለበት ተሰማት፡፡‹‹የእኔ ፍቅር አሁን ደግሞ ያንተ ተራ ነው..አምጣ ሳሙናውን ልሽህ፡፡››አለችና ከስሩ ሸሸት ብላ ሳሙናውን ከእጁ ተቀበለች፡፡የሻወሩን ውሀ ከፈተችና ሰውነቱን በውሀ እንዲያስመታ ዞር አለችለት፡፡ከፀጉሩ ጀምሮ ሳሙና አስመታና ‹‹በይ እሺኛ ››በማለት ደረቱን ዘርግቶ ወደእሷ ተጠጋ…
‹‹የእኔ ፍቅር ደረትህንማ አንተው በቀላሉ ማሸት ትችላለህ..ጅርባህን ዙርና እሱን ልሽህ››አለችው፡፡እንዳለችው በዝምታ ዞረ፡፡ ጀርባውን ከትከሻው ጀምሮ የፓንቱ ጠርዝ እስኪሚታይበት እስከመቀመጫው ድረስ አሸችውና..‹‹እንካ ጠጋ በልና ፊት ለፊትህን ሰሙና ምታው ..እስከዛ እኔ ልለቃለቅ›› ብላ ሳሙናውን አቀበለችውና የሻወሩን ቧንቧ በመክፈት ሰውነቷን ተለቃለቀች፡፡ድምፅ ሳታወጣ በምልክት ፊቱን ከእሷ እንዲያዞር አዘዘችው…ቅር እያለው ዞረ ፡፡ፓንቷን አወለቀችና መስቀያው ላይ አንጥልላ አንድ ፎጣ ከመስቀያው ላይ አንስታ በእጇ በመያዝ ባዶ መቀመጫዋን እያማታች ከሻወር ቤት ወጣች…እሱም ጥላው እንደወጣች ሲያውቅ ፈጠን አለና ሰውነቱን የሰተለቀለቀውን ሳሙና መለቃለቅ ጀመር…፡፡
ፎጣውን አገልድማ መውጣት እንዳለባት ታውቃለች.፡፡ግን ደግሞ እሷ እንደገመተችው እዚህ ድረስ ያስመጧቸው ሰዎች እዚህ ክፍል ውስጥ ካሜራ ካስቀመጡና እየተከታተሏቸው ከሆነ ከናኦል ጋር ባልና ሚስት እንደሆኑ ይበልጥ ማሳመን አለባት፡፡እርግጥ ለማንም ሰው በተለይ ለአንዲት ሴት በሆነ ቴክኖሎጂ ሰዎች ከርቀት ሆነው እየቀረፃት እንደሆነ እየተጠራጠረች , እርቃኗን በነፃነት የምታሳይ ሴት አትገኝም፡፡እሷ ግን ለዚህ የሰለጠነች ነች፡፡የሆነ የተሰማራችበትን ተልዕኮ ተግባራዊ ለማድረግ እስከጠቀመ ድረስ ማንኛውንም አይነት የተቀናጀ ተግባሮችን መፈፀም እንዳለባት ታውቃለችም ..ያንን ብዙ ጊዜ ተግባራዊ አድርጋ ውጤት አስመዝግባበታለች…አሁንም እያደረገችው ያለው ተመሳሳይ ነው…የትኛውም ወንድ እንዲህ የሴት እርቃን ገላ እየተመለከተ ጥርት ያለ ሀሳብ ሊያስብ አይችልም፡፡ስሌቷ እንደዛ ነው፡፡
ሰውነቷን በፎጣው አደራረቀቸና ሌላ ቅያሪ ፓንት ከቦርሳዋ አውጥታ እየለበሰች ሳለ ..እሱም ልክ እንደ እሷ በቅጡ ያልተላጨ የተሸፈነ እንትኑን እያማታ መጣ፡፡በቆሪጥ አይታው ወደሻንጣዋ አቀረቀረችና የምትለብሰውን ልብስ መምረጥ ጀመረች፡፡ተጠቅማ ጠረጴዛው ላይ ያስቀመጠችውን ፎጣ እያነሳ…‹‹ማሬ ሰውነቴን በዚህ ላደራርቅ እንዴ?›› ሲል ጠየቃት..፡፡
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ብራዚል/ፔሩ
ናኦል እና ምስራቅ የወደቧ ውብ ከተማ ሪዬ ዲጄኔሮ እንደደረሱ ቀጥታ ታክሲ ይዘው ወደ ሆቴል ነው ያመሩት፡፡ለሁለትም እንዲህ አይነት ረጅም የአየር ላይ ጉዞ ሲጓዙ የመጀመሪያቸው ስለሆነ ድካሙ ከልክ ያለፈ ነበር..በተለይ ናኦል ከሀገር ውስጥ በረራዎች በስተቀር ድንበር ሲሻገር እራሱ የመጀመሪያው ገጠመኙ ሰለሆነ ጉዞ እንደህልም ነው የሆነበት ፡፡ሁለቱ ከአየር መንገድ ወጥተው ታክሲ ተሳፍረው ወደሆቴል እየሄዱ እያሉ ከሻንጣዋ የጎን ኪስ አንድ ወረቀት አወጣችና አቀበለችው፡፡
ተቀብሎ እያያት‹‹ምንድነው?፡፡››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አንብበው፡፡››
የተጣጠፈውን ወረቀት ገለጠና አየው..ከወረቀቱ ጫፍ በግራ በኩል የእሱ ፎቶ ተለጥፎበታል፡፡ በተመሳሳይ መስመር በቀኝ በኩል ደግሞ የራሷ የምስራቅ ፎቶ አለበት፡፡በመደነቅ እንደተሞላ ማንበብ ጀመረ‹‹ሁለቱ ባልና ሚስት እንደሆኑ የሚያወራና ያንንም የሚያረጋግጥ ህጋዊ የጋብቻ ሰርተፍኬት ነው፡፡ባለማመን አይኑን ጨፈን ገለጥ ጨፈን ገለጥ በማድረግ ደጋግሞ አየው፡፡ትክክል ነው፡፡
‹‹ውይ እኔ እኮ በጣም እድለኛ ሰው ነኝ ..መቼ ነው ህልሜ እንዲህ ያሳከሁት?መቼ ነው በአለም ላይ እጅግ የማደንቃትንና የምወዳትን የህልሜን ሴት ያገባሁት….?እስኪ ንገሪኝ መቼ ነው ?››
‹‹ጎረምሳው አረጋጋው..ይሄ ኑሀሚን በመፈለግ ሂደት በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ስለሆነ ነው፡፡ይሄንን ተልዕኮችን እስኪጠናቀቅ እኔና አንተ ባልና ሚስት ነን፡፡የተጋባንበትን ቀን በቃልህ ሸምድደው..ሁለት ወር ሆኖናል፡፡ገና ትኩስ ባለትዳሮች ነን፡፡እንኳ…ደግሞ ቀለበትን በትከክለኛ እጣትህ ላይ አጥልቀው›› አለችናን እጇ ላይ ካለው ሁለት ቀለበት መካከል አንድን አቀበለችው፤ ሁለተኛውን እራሷ ጣት ላይ አጠለቀች፡፡ተቀበላትና በሚፍለቀለቅ ፈገግታው ታጅቦ ቀለበቱን አጠለቀው፡፡
‹‹…ይሄው..አሁን ሁሉ ነገር ውብና ፍፅም ትክክል ሆኗል…ግን ይሄንን ሰርተፍኬት እኔ ጋር ቢሆን ምን ይመስልሻል?››
‹‹ግድ የለም ያዘው ..የረሴ ድርሻ አለኝ..››አለችው በፈገግታ፡፡
ከዛ ሆቴል ደርሰው በባልና ሚስት ተመዝግበው አንድ አልጋ ያለው መኝታ ክፍል ያዙ፡፡ከምስራቅ ጋር በጣም በርካታ ቀናቶች ተመሳሳይ ቤት ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ክፍሎችና የተለያዩ አልጋዎች ላይ የመተኛት አጋጣሚ ቢኖራቸውም እንዲህ አንድ አልጋ ላይ የመተኛት እድል አጋጥሞት አያውቅም….አሁን ያ እድል እውን ሊሆንለት እንደሆነ ሲያስብ ልቡ በውስጡ መፈንጠዝ ጀመረች፡፡
///
በማግስቱ ከብራዚል ወደፔሩዋ ከተማ ሊማ ተጓዙና ምንም ሳያርፍ ቀጥታ ወደኢኩዬቶስ በረሩ…እንደደረሱ ለኡበሩ ሹፌር የተነገራቸውን ሆቴል ስም ነገሩና ወደዛው ወሰዳቸው፡፡ልክ ከኡበሩ የየራሳውን ሻንጣ ይዘው ወረዱና ወደሆቴል መጓዝ ሲጀምሩ‹‹እንግዲህ ከእስከአሁኑ በላይ በጣም ጠንቃቃ ሁኑ ..ከዚህ ሰዓት ጀምሮ በእርግጠኝነት በእነሱ ሰዎች እይታ ስር ነው ያለነው…ሆቴሉ ውስጥም ሆነ የምንገባበት መኝታ ቤት ውስጥ ካሜራ እንደሚያስቀምጡ እርግጠኛ ነኝ፡፡››አለችው፡፡
‹‹ገባኝ..እጠነቀቃለሁ፡፡››
‹‹ሆቴል ብክ አደረጉና ፅዱ የሆነ ባለአንድ አልጋ መኝታ ቤት ተሰጣቸው፡፡ገብተው ዕቃቸውን አመቻችተው እንዳስቀመጡ..‹‹የእኔ ፍቅር ትንሽ ሞቆኛል ሻወር ልወስድ ነው..አስከዛው ጋደም ብለህ ጠብቀኝ ..››አለችና እዛው እያያት ልብሷን በማወላለቅ እርቃኗን ሰውነቷ ላይ በቀረ ሰማያዊ ፓንት ብቻ ወደ ሻወር ቤት ሄደች፡፡እሱም በፍዘት ሲያያት ቆይቶ ሻወር ቤት ገብታ እስክትሰወርበት እየተመለከታት ነበር.፡፡ሌላ ቀን እዛ ሀገራቸው ምድር ላይ ሆኖ እንደዚህ ፊት ለፊቱ ልብሷን አወላልቃ እንዲህ እርቃኗን ቆማ አይቷት ቢሆን ኖሮ ወይ ተንደርድሮ ሄዶ ይጠመጠምባታል..ወይ ደግሞ እራሱን ስቶ መሬት ይዘረር ነበር፡፡አሁን ግን ከደቂቃዎች በፊት ያስጠነቀቀችውን እያሰበ እራሱን በትልቅ ጥረት ተቆጣጥሮ በትግስት ባለበት መርጋት ቻለ..፡፡
እሷ እየሰራች ያለውን ድራማ ይበልጥ ሊያደምቀው ወሰነና ልክ እሷ እንዳደረገችው ልብሱን አወላለቀ እና በፓንቱ ብቻ ወደሻወር ቤት ሄደና ገርበብ ያለውን በራፍ ገፋ በማድረግ ወደውስጥ ገባ ፡፡አልጠበቀችም ነበርና ስታየው ደነገጠች፡፡ሰውነቷን ስታሽበት የነበረው ሳሙና ከእጇ ተንሸራተተና ወደወለሉ ወደቀባት፡፡
‹‹የእኔ ፍቅር ላሽሽ እኮ ነው የመጣሁት…››አለና ሳሙናውን ጎንበስ ብሎ በማንሳት ሰውነቷን በአራፋው ያዳርስ ጀመር፡፡እሱ ብቻ ሳይሆን እሷም እጆቹ ሰውነቷ ላይ ሲሽከረከሩ ድንዝዝ እያለች ነው፡፡ልትቆጣጠረው የማትችል ስሜት በውስጧ ሲንተከተክና ልቧን ድክምክም ሲያደርጋት እየታወቃት ነው፡፡በዚህ ስሜት ተሸንፋ ዝልፍልፍ ብላ ክንዱ ላይ ከመውደቋ እና ባሳደገችው ልጅ ፊት ከመዋረዷ በፊት የሆነ ነገር ማድረግ እንዳለበት ተሰማት፡፡‹‹የእኔ ፍቅር አሁን ደግሞ ያንተ ተራ ነው..አምጣ ሳሙናውን ልሽህ፡፡››አለችና ከስሩ ሸሸት ብላ ሳሙናውን ከእጁ ተቀበለች፡፡የሻወሩን ውሀ ከፈተችና ሰውነቱን በውሀ እንዲያስመታ ዞር አለችለት፡፡ከፀጉሩ ጀምሮ ሳሙና አስመታና ‹‹በይ እሺኛ ››በማለት ደረቱን ዘርግቶ ወደእሷ ተጠጋ…
‹‹የእኔ ፍቅር ደረትህንማ አንተው በቀላሉ ማሸት ትችላለህ..ጅርባህን ዙርና እሱን ልሽህ››አለችው፡፡እንዳለችው በዝምታ ዞረ፡፡ ጀርባውን ከትከሻው ጀምሮ የፓንቱ ጠርዝ እስኪሚታይበት እስከመቀመጫው ድረስ አሸችውና..‹‹እንካ ጠጋ በልና ፊት ለፊትህን ሰሙና ምታው ..እስከዛ እኔ ልለቃለቅ›› ብላ ሳሙናውን አቀበለችውና የሻወሩን ቧንቧ በመክፈት ሰውነቷን ተለቃለቀች፡፡ድምፅ ሳታወጣ በምልክት ፊቱን ከእሷ እንዲያዞር አዘዘችው…ቅር እያለው ዞረ ፡፡ፓንቷን አወለቀችና መስቀያው ላይ አንጥልላ አንድ ፎጣ ከመስቀያው ላይ አንስታ በእጇ በመያዝ ባዶ መቀመጫዋን እያማታች ከሻወር ቤት ወጣች…እሱም ጥላው እንደወጣች ሲያውቅ ፈጠን አለና ሰውነቱን የሰተለቀለቀውን ሳሙና መለቃለቅ ጀመር…፡፡
ፎጣውን አገልድማ መውጣት እንዳለባት ታውቃለች.፡፡ግን ደግሞ እሷ እንደገመተችው እዚህ ድረስ ያስመጧቸው ሰዎች እዚህ ክፍል ውስጥ ካሜራ ካስቀመጡና እየተከታተሏቸው ከሆነ ከናኦል ጋር ባልና ሚስት እንደሆኑ ይበልጥ ማሳመን አለባት፡፡እርግጥ ለማንም ሰው በተለይ ለአንዲት ሴት በሆነ ቴክኖሎጂ ሰዎች ከርቀት ሆነው እየቀረፃት እንደሆነ እየተጠራጠረች , እርቃኗን በነፃነት የምታሳይ ሴት አትገኝም፡፡እሷ ግን ለዚህ የሰለጠነች ነች፡፡የሆነ የተሰማራችበትን ተልዕኮ ተግባራዊ ለማድረግ እስከጠቀመ ድረስ ማንኛውንም አይነት የተቀናጀ ተግባሮችን መፈፀም እንዳለባት ታውቃለችም ..ያንን ብዙ ጊዜ ተግባራዊ አድርጋ ውጤት አስመዝግባበታለች…አሁንም እያደረገችው ያለው ተመሳሳይ ነው…የትኛውም ወንድ እንዲህ የሴት እርቃን ገላ እየተመለከተ ጥርት ያለ ሀሳብ ሊያስብ አይችልም፡፡ስሌቷ እንደዛ ነው፡፡
ሰውነቷን በፎጣው አደራረቀቸና ሌላ ቅያሪ ፓንት ከቦርሳዋ አውጥታ እየለበሰች ሳለ ..እሱም ልክ እንደ እሷ በቅጡ ያልተላጨ የተሸፈነ እንትኑን እያማታ መጣ፡፡በቆሪጥ አይታው ወደሻንጣዋ አቀረቀረችና የምትለብሰውን ልብስ መምረጥ ጀመረች፡፡ተጠቅማ ጠረጴዛው ላይ ያስቀመጠችውን ፎጣ እያነሳ…‹‹ማሬ ሰውነቴን በዚህ ላደራርቅ እንዴ?›› ሲል ጠየቃት..፡፡
👍66❤7
ለመልበስ መርጣ በእጇ ይዛ ነበረውን ጅንስ ሱሪ አልጋው ጠርዝ ላይ ወርወር አደረገችና‹‹አዎ ማሬ..ቆይ እንደውም እኔ ልርዳህ›› አለችና ወደእሱ በመንቀሳቀስ ፎጣውን ከእጁ ላይ ተቀበለችና መላ ሰውነቱን በፎጣው እያሻሸች ታደራርቅለት ጀመር፡፡
‹‹አይበቃህም?››፡፡አለችው
ወደእሷ ዞረና አቀፎ ከእርቃን ሰውነቱ ጋር አጣበቃት…ያለምንም ተቃውሞ ልጥፍ አለችበት…በእድሜ ከ15 ኣመት በላይ ትብለጠው እንጂ በቁመት ከ15 ሴ.ሜትር በላይ ይበልጣታል…ወደታች ጎንበስ አለና አፉን ወደአፏ አሞጠሞጠ…ቀና ብላ ከንፈሯን በማቅናት ተቀበለችው፡፡፡
ለ5 ደቂቃ ያለማቋረጥ ተሳሳሙና ሲላቀቁ ሁለቱም እራሳቸውን ችለው መቆም አቅቷቸው ነበር…በናኦል ጭንቅላት ውስጥ ሲመላለስ የነበረው ሙሉ በሙሉ ተሸክሞ አልጋ ላይ መጣልና የለበሰችውን ፓንት መልሶ አውልቆ ጥሎ ያንን ለዘመናት ሲማልልለት የኖረውን ጭኗ መካከል አካሉን ብቻ ሳይሆን ነፍሱንም ጭምር በመክተት መጥፋት ነበር…እንደዛ ቢያደርግ እሷም ብትሆን እንደማትቃወመውና እንዳደረጋት እንደምትሆን እርግጠኛ ነው..ግን ከዛ በኃላ ባላቸው የወደፊት ግንኙነት ላይ ምን አይነት ጥቁር ነጥብ እንደሚጥል እርግጠኛ መሆን ስላልቻለና ከምንም በላይ የእህቱን ደህንነት የማረጋገጥና የት እንደሆነች የማወቅ ሂደት ላይ የሚያመጣውን ተፅእኖ አሉታዊ ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት ስላደረበት እንደምንም ብሎ ስሜቱን መግታትና የውስጥ ረሀቡን ማክሰም ቻለ፡፡
ምስራቅም ለተወሰነ ሰከንድ ትንፋሽ ከወሰደች በኃላ በፍጥነት ከተቀመጠችበት የአልጋው ጠርዝ ተነስታ አጠገቧ ያለውን ጅንስ ሱሪ ለበሰች…ከዛ ከላይ ፓካውትና ጃኬት ደረበች፡፡እሱም እሷን ተከትሎ ልብሱን ከሻንጣው እየመረጠ ለብሶ ካጠናቀቀ በኃላ፡፡
‹‹እሺ አሁን ቀጣይ እቅዳችን ምንድነው?››
‹‹መጀመሪያ ስልክህ አውጣና ..ለሰዎቻችን መልዕክት ላክላቸው፡፡››
ስልኩን ቀድሞ ካወለቀው ሱሪ ውስጥ አወጣና ከፈተ‹‹ምን ብዬ ነው የምፅፈው?››
‹‹ያው በተባባልነው መሰረት መጥቼ ኢኩያቶስ ገብቼ ያላችሁኝ ሆቴል አርፌለው…መች ነው የምንገናኘው?››ብለህ ላክላቸው፡፡
‹‹እሺ›› አለና ያለችውን በእንግሊዘኛ ፅፎ ላከላቸው፡፡ ከአምስት ደቂቃ በኃላ መልስ መጣለት
‹‹እንኳን ሰላም መጣህ… ዛሬ ዞር ዞር ብለህ ከተማዋን እያት…እርፍት ውሰድ ነገ እናገኝሀለን፡፡››ይላል፡፡
የመጣለትን ጽሁፍ ቀድሞ ካነበበ በኃላ እሷም እንድታነበው ስልኩን አቀበላት..አነበበችውና ስልኩን እየመለሰችለት፡፡ከተቀመጠችበት ተነስታ ፊት ለፊቷ ቆመችና ሆዷን እያሻሸች ‹‹አየህ የእኔ ፍቅር ..ነገ ማለት ብዙ እሩቅ አይደለም…ኑሀሚን እናገኛታለን፡፡ሶስታችንም አብረን ወደሀገራችን እንመለሳለን.. ከዛ ሴት ልጅ አረግዝልሀላው፡፡አንተንም አባት እሷንም አክስት አደርጋችኋለው፡፡፡፡››አለችው
‹‹ተስፋ አደርጋለው የእኔ ፍቅር.. አሁን እርቧኛል ..ወጥተን የሆነ የሚበላ ነገር እንፈለግ››አለት፡፡
‹‹አዎ …ተነስ እንሂድ….››አለችውና እጁን ይዛ ከክፍሉ ወጡ፡፡ቀጥታ ወደ ሆቴሉ ነው የወረዱት፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
በዛውም list ሊሆን 24 ቀን ብቻ የቀረውን Airdrop ላይ ተሳተፉ ብዙ ሰው እየተሳተፈ ነው👇👇👇👇
1 t.me/empirebot/game?startapp=hero405867113
🔥Play with me, grow your startup.
💸 +5k coins as your first gift
💵 +25k coins if you have Telegram Premium
2 https://xn--r1a.website/major/start?startapp=405867113
👑 Join me in @Major game and earn $MAJOR token soon!
⭐️ 750 rating bonus for you.
⭐️ 1000 rating bonus if you are Premium.
‹‹አይበቃህም?››፡፡አለችው
ወደእሷ ዞረና አቀፎ ከእርቃን ሰውነቱ ጋር አጣበቃት…ያለምንም ተቃውሞ ልጥፍ አለችበት…በእድሜ ከ15 ኣመት በላይ ትብለጠው እንጂ በቁመት ከ15 ሴ.ሜትር በላይ ይበልጣታል…ወደታች ጎንበስ አለና አፉን ወደአፏ አሞጠሞጠ…ቀና ብላ ከንፈሯን በማቅናት ተቀበለችው፡፡፡
ለ5 ደቂቃ ያለማቋረጥ ተሳሳሙና ሲላቀቁ ሁለቱም እራሳቸውን ችለው መቆም አቅቷቸው ነበር…በናኦል ጭንቅላት ውስጥ ሲመላለስ የነበረው ሙሉ በሙሉ ተሸክሞ አልጋ ላይ መጣልና የለበሰችውን ፓንት መልሶ አውልቆ ጥሎ ያንን ለዘመናት ሲማልልለት የኖረውን ጭኗ መካከል አካሉን ብቻ ሳይሆን ነፍሱንም ጭምር በመክተት መጥፋት ነበር…እንደዛ ቢያደርግ እሷም ብትሆን እንደማትቃወመውና እንዳደረጋት እንደምትሆን እርግጠኛ ነው..ግን ከዛ በኃላ ባላቸው የወደፊት ግንኙነት ላይ ምን አይነት ጥቁር ነጥብ እንደሚጥል እርግጠኛ መሆን ስላልቻለና ከምንም በላይ የእህቱን ደህንነት የማረጋገጥና የት እንደሆነች የማወቅ ሂደት ላይ የሚያመጣውን ተፅእኖ አሉታዊ ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት ስላደረበት እንደምንም ብሎ ስሜቱን መግታትና የውስጥ ረሀቡን ማክሰም ቻለ፡፡
ምስራቅም ለተወሰነ ሰከንድ ትንፋሽ ከወሰደች በኃላ በፍጥነት ከተቀመጠችበት የአልጋው ጠርዝ ተነስታ አጠገቧ ያለውን ጅንስ ሱሪ ለበሰች…ከዛ ከላይ ፓካውትና ጃኬት ደረበች፡፡እሱም እሷን ተከትሎ ልብሱን ከሻንጣው እየመረጠ ለብሶ ካጠናቀቀ በኃላ፡፡
‹‹እሺ አሁን ቀጣይ እቅዳችን ምንድነው?››
‹‹መጀመሪያ ስልክህ አውጣና ..ለሰዎቻችን መልዕክት ላክላቸው፡፡››
ስልኩን ቀድሞ ካወለቀው ሱሪ ውስጥ አወጣና ከፈተ‹‹ምን ብዬ ነው የምፅፈው?››
‹‹ያው በተባባልነው መሰረት መጥቼ ኢኩያቶስ ገብቼ ያላችሁኝ ሆቴል አርፌለው…መች ነው የምንገናኘው?››ብለህ ላክላቸው፡፡
‹‹እሺ›› አለና ያለችውን በእንግሊዘኛ ፅፎ ላከላቸው፡፡ ከአምስት ደቂቃ በኃላ መልስ መጣለት
‹‹እንኳን ሰላም መጣህ… ዛሬ ዞር ዞር ብለህ ከተማዋን እያት…እርፍት ውሰድ ነገ እናገኝሀለን፡፡››ይላል፡፡
የመጣለትን ጽሁፍ ቀድሞ ካነበበ በኃላ እሷም እንድታነበው ስልኩን አቀበላት..አነበበችውና ስልኩን እየመለሰችለት፡፡ከተቀመጠችበት ተነስታ ፊት ለፊቷ ቆመችና ሆዷን እያሻሸች ‹‹አየህ የእኔ ፍቅር ..ነገ ማለት ብዙ እሩቅ አይደለም…ኑሀሚን እናገኛታለን፡፡ሶስታችንም አብረን ወደሀገራችን እንመለሳለን.. ከዛ ሴት ልጅ አረግዝልሀላው፡፡አንተንም አባት እሷንም አክስት አደርጋችኋለው፡፡፡፡››አለችው
‹‹ተስፋ አደርጋለው የእኔ ፍቅር.. አሁን እርቧኛል ..ወጥተን የሆነ የሚበላ ነገር እንፈለግ››አለት፡፡
‹‹አዎ …ተነስ እንሂድ….››አለችውና እጁን ይዛ ከክፍሉ ወጡ፡፡ቀጥታ ወደ ሆቴሉ ነው የወረዱት፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
በዛውም list ሊሆን 24 ቀን ብቻ የቀረውን Airdrop ላይ ተሳተፉ ብዙ ሰው እየተሳተፈ ነው👇👇👇👇
1 t.me/empirebot/game?startapp=hero405867113
🔥Play with me, grow your startup.
💸 +5k coins as your first gift
💵 +25k coins if you have Telegram Premium
2 https://xn--r1a.website/major/start?startapp=405867113
👑 Join me in @Major game and earn $MAJOR token soon!
⭐️ 750 rating bonus for you.
⭐️ 1000 rating bonus if you are Premium.
👍49❤9👏1
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ከተማው ውስጥ ሲዞዞሩና በከፊል የተጨነቀ በከፊል ደግሞ በከተማዋ ውበት ልብ የተሰረቀ ጥንድ ባልና ሚስቶችን ገፀ ባህሪ እየተጫወቱ አመሹ ፡፡ምሽት ላይ አዛው አልጋ የያዙበት ሆቴል መጠጥ እየቀማመሱና እየተጫወቱ ሰዓቱን ከገፉት በኃላ አራት ሰዓት አካባቢ ከተወሰነ ሞቅታ ጋር ወደ መኝታቸው ተመለሱ፡፡እንደገቡ እሷ የለበሰችውን ልብስ አውልቃ ስስ ቢጃማ ቀሚሶን ለበሰችና ተበትኖ የዋለውን ፀጉሯን አንድ ላይ አሲዛ በጨርቅ በማሰር አንሶላውን ገልጣ ከውስጥ ገባች..እሱም በተመሳሳይ የለበሰውን ልብስ አወላለቀና ወደሻንጣው ሄደ፡፡ ሀሳብ እሷ እንዳደረገችው ቢጃማ ፈልጎ ሊለብስ ነበር…ግን በህይወቱ ቢጃማ ለብሶ የመተኛት ልምድ ስለሌለው ቀጥታ ሰውነቱ ላይ በቀረው ፓንት ብቻ ወደአልጋው ሄደ፡፡ ብርድልብሱንና አንሶላውን ገለጠና ከስር ገባ …ወደእሱ ዞረች…ሰውነታቸው ሲነካካ የሁለቱም የሙቀት መጠን ወደላይ ተስፈነጠረ፡፡እሱ ክንዶቹን በአንገቷ ስር ሰቅስቆ አስገባና አቀፋት ..አንገቷን ከትራሱ ላይ ቀና አደረገችና ደረቱ ላይ ተኛች፡፡በአንገቷ ስር የተሻገረው እጁ ተመለሰና በከፊል የተጋለጠው ቀኝ ጡቷ ላይ አረፈ…፡፡ጭንቅላቷ ድረስ ነዘራት፡፡
አካሄዱ ስላላማራት በጥበብ አእምሮውን በመበታተን ልታስቆመው አሰበች..‹‹የእኔ ፍቅር ኑሀሚ እዚህ ከተማ ያለች ይመስልህል?፡፡››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ እዚህ ያለች ይመስለኛል››በእርግጠኝነት መለሰላት፡፡
‹‹ታዲያ ለምን ዛሬውኑ ሳያገናኙን?››
‹‹ያው ምንም ቢሆን እነሱ ባሉት መሰረት ብቻችንን እንደመጣን እስኪያረጋግጡ መሰለኝ››
‹‹እንዴ ምን ነካሽ? በእህታችን ነፍስ እንዴት ቁማር መጫወት እንችላለን…?የአካባቢው መንግስት አቅም ቢኖረው እኮ እስከአሁን ያገኛትና ወደሀገሯ ይመልሳት ነበር፡፡››
‹‹እሱስ እወነትህን ነው..ይሄንን ምናውቀው ግን እኛ ነን..እነሱ የሆነ ነገር ያደርጋሉ ብለው ቢጠረጥሩ ስህተት አልሰሩም፡፡››
‹‹ይሁን እንዳልሽ፡፡እርግጠኛ ነኝ ነገ ብቻችንን መሆናችንን በራሳቸው መንገድ ያረጋግጡና ከእህቴ ያገናኙኛል የሚል እምነት አለኝ››
‹‹አንተ ..››አለችና በድንጋጤ ከደረቱ ላይ ተነሳታ ንግግሯን አራዘመች‹‹ሚስቴ አብራኝ ትመጣለች ብልህ ነግረሀቸዋል እንዴ?››ያላሰበውን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
እሷ ድራማውን በደንብ አድርጋ እየተጫወተችና እነሱ ጋር እንዲደርስላት የምትፈልገውን መልእክት እንዲናግር ሂሳቡን በመስራት ነበር ጥያቄዎችን የምታቀርብለት..እሱ ግን የእሷ ከእሱ ተከትሎ ፔሩ ድረስ መምጣት ከሰዎቹ ጋር ባደረገው በእስከአሁኑ ንግግራቸውም ሆነ ስምምነታቸው ላይ ስላልነበረ..ይሄ በራሱ እንቅፋት እንዳይሆንባቸው ስለፈራ ደነገጠ፡፡
‹‹አንቺ እስከአሁን ማሳወቅ ነበረብኝ…ምን አይነት የማረባ ሰው ነኝ››አለና ከተኛበት በመነሳት አልጋውን ለቆ ወረደ…
‹‹ወደየት ልትሄድ ነው?››
‹‹ነገ ሲመጡ አይተውሽ ሌላ አለመግባባት ውስጥ ከምንገባ አሁኑኑ በኢሜል ላሳውቃቸው፡፡››
ከተኛችበት ሆና ‹‹ጥሩ አስበሀል ማሬ… ፃፈላቸው፡፡››ስትል ፍቃድ ሰጠችው፡፡
እስከአሁን ሳልነግራችሁ የዘነጋሁት አንድ ጉዳይ አለ፡፡ይቅርታ..ባለቤቴ ወደማላውቀው ሀገር ብቻዬን ልትልከኝ ፍቃደኛ ስላልሆነች አብራኝ ተከትላኝ መጥታለች..ቀድሜ ላሳውቃችሁ ብዬ ነው፡፡››
ብሎ ፃፈና ላከው፡፡እና ሞባይሉን ይዞ ወደአልጋው ተመልሶ በመሄድ ከውስጥ ገብቷ ተኛና ምስራቅን መልሶ አቀፎት ለላከው መልዕክት መልስ ይጠብቅ ጀመር፡፡ወዲያው የኢሜሉን መልእክት መልስ መጣለት፡፡
ቀድመህ ልታሳውቀን ይገባ ነበር…ደግመህ ከተስማማንበት ውጭ የሆነ አንዲት ቅንጣት ነገር ብታደርግ እህትህን ማግኘቱን እርሳው፡፡ለጊዜው የሚስትህን መምጣት ተቀብለነዋል፡፡ግን ደግሞ ለአንተ የነገርናቸውን ማስጠንቀቂያዎች እሷም እንድታከብር የማድረግ ኃላፊነቱ ያንተው ነው፡፡
ይላል ፡፡ምስራቅንም አስነበባትና ስልኩን አስቀምጦ መብራቱን አጠፋና አቅፎት ተኛ… ወደጆሮዋ ጠጋ ብሎ በሹክሹክታ‹‹ደህና እደሪ››አላት
‹‹እንቅልፍህ መጣ እንዴ?››
‹‹አይ አልመጣም..የሚመጣም አይመስለኝም..እኚ ሰዎች እስከአሁን ሙሉ በሙሉ ያመኑን አይመስለኝም፣ማለቴ ባልና ሚስት መሆናችንን›› አለችው፡፡
ጆሮዋ ላይ ተለጥፎ‹‹አረ ያምኑናል…እንዲህ እየሆን እንዴት ላያምኑን ይችላሉ? ››
‹‹ባልና ሚስቶች እንዲህ ብቻ አይደለም የሚሆኑት፡፡ይህንን አታውቅም እንዴ? ››
ምን ለማለት እደፈለገች ቢገባውም ያልገባው ለመምሰል ሞከረ ‹‹እንደምታውቂው ከዚህ በፊት አግብቼ አላውቅም… እንዴት ላውቅ እችላለሁ?››
‹‹ለማወቅ እኮ ማግባት አይጠበቅብህም››አለችው በሹክሹክታ
‹‹ታዲያ ምን ይሻለናል እያልሽ ነው?››
‹‹ኑሀሚን አደጋ ላይ የሚጥል ምንም አይነት ስህተት መስራት የለብንም፡፡ አሁን እንተሻሻለን››
..ቀስ ብዬ ልብሴን አወልቅና ወደወለሉ ወረውራለው፡፡ አንትም ፓንትህን ታወልቃለህ ….እኔ ጭን መካከል ትገባለህ..ልክ ወሲብ እንደሚያረግን ባልና ሚስት በንቅናቄና በድምፅ ማስመሰል እንቀጥላለን..ግን በምንም አይነት ሁኔታ እትንህን ጭኔ ውስጥ የእውነት ለመክተት እንዳትሞክር››
‹‹ተንሸራቶ ከገባብኝስ?››
‹‹ወደሀገራችን ስንመለስ ግንባርህን በሽጉጥ አፈርሰውና ባርቆብኝ ነው ብዬ ቃል እሰጣለሁ፡፡››
‹‹ተስማምቼለሁ›› አለና ሙሉ በሙሉ ወደእሷ በመዞር ከሰውነቱ አጣብቆ ያሻት ጀመረ..እሷም ቀስ በቀስ እያደገ እና እየጨመረ በሚሄድ በተቆራረጠ ድምፅ በማጀብ እጆቾን በእርቃን ሰውነቱ ላይ ታመላለስ ጀመር…ድምፃቸው ምን አልባት እየቀረፃቸው ያለው መቅራጫ በጭለማ ምስል ማስቀረት ባይችል እንኳን ወሲብ ላይ መሆናቸውን የሚያበስረውን ድምጽ በትክክል ማስቀረት ስላለበት በደንብ ነበር የተወኑት ፡፡ከ10 ደቂቃ መተሻሸት በኃላ እሷ ቀድማ ከእቅፉ ወጣችና የለበሰችውን ቢጃማ ሆነ ፓንት አወቀለቀችና ወለል ላይ ወረወችው..እሱም ፓንቱን አወለቀና ተመሳሳዩን አደረገ ..ሙሉ በሙሉ እርቃናችውን እርስ በርስ ተጣበቁ ..እሱ ግን የተሰጠውን ትዕዛዝ ማክበር አልቻለም፡፡ከ5 ደቂቃ መፋተግ በኃላ የእሷም ብልት በፈሳሽ መረጣጠቡን ተከትሎ ሙከራው ከሸፈበትና ብልቱ አዳልጦት ከማንነቷ ጋር ሙሉ በሙሉ ተዋሀዳት..ሁለቱም የሆነውን ያወቁት የመጨራሻ ጡዘት ላይ ደርሰው በእርካታ ወደ ስሜታቸው ስክነት ከተመለሱ በኃላ ነው፡፡ምንም አላላች፡፡ከተወሰነ ደቂቃዎች እረፍት በኃላ ሰውነቷ ላይ የነበረውን ብርድልብስ ገፋ አስወገደችና ከአልጋው ወርዳ ወደግድግዳው በመሄድ መብራቱን አበራችው..ይሄንን ሆነ ብላ ነው ያደረገችው..ናኦል ዝርግትግት ብሎ እርቃኑን አልጋው ላይ ተኝቷል ..ቀጥታ ወደሻወር ቤት ሄደች፡፡
ሻወር ቤት ገባችና ውሀውን ከፈተች፡፡ መሀከል አናቷን ማስመታት ጀመረች…አሁን ያደረገችው ነገር ምን እንደሚያመጣባት ምንም እርግጠኛ መሆን አልቻለችም…እሷ በህይወቷ ከመቶ በላይ የማትፈልጋቸውን ወሲባዊ ተራክቦ ከብዙ የማትፈልጋቸው ሰዎች ጋር አድርጋ ታውቃለች፡›ቀድሞውንም አእምሮዋን አሳምና ስለምትከውነው ምንም አይነት የመንፈስ ቁስለት ሆነ ፀፀት አስከትሎባት አያውቅም ነበር፡፡ይሄ የአሁኑ ግን ከአነዛ በጣም የተለየ ነው፡፡ በመጀመሪያ ይሄን ልጅ ገና ከ12 ዓመቱ ጀምሮ ታውቃዋለች፡፡ እያንዳንዱን እንቅስቃሴውን ለውጡን እድገቱን በቅርበት ስትከታተል ነው የኖረችው…ልክ እንደታላቅ እህቱ ስትንከባከበው እና ስትጠብቀው ነው
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ከተማው ውስጥ ሲዞዞሩና በከፊል የተጨነቀ በከፊል ደግሞ በከተማዋ ውበት ልብ የተሰረቀ ጥንድ ባልና ሚስቶችን ገፀ ባህሪ እየተጫወቱ አመሹ ፡፡ምሽት ላይ አዛው አልጋ የያዙበት ሆቴል መጠጥ እየቀማመሱና እየተጫወቱ ሰዓቱን ከገፉት በኃላ አራት ሰዓት አካባቢ ከተወሰነ ሞቅታ ጋር ወደ መኝታቸው ተመለሱ፡፡እንደገቡ እሷ የለበሰችውን ልብስ አውልቃ ስስ ቢጃማ ቀሚሶን ለበሰችና ተበትኖ የዋለውን ፀጉሯን አንድ ላይ አሲዛ በጨርቅ በማሰር አንሶላውን ገልጣ ከውስጥ ገባች..እሱም በተመሳሳይ የለበሰውን ልብስ አወላለቀና ወደሻንጣው ሄደ፡፡ ሀሳብ እሷ እንዳደረገችው ቢጃማ ፈልጎ ሊለብስ ነበር…ግን በህይወቱ ቢጃማ ለብሶ የመተኛት ልምድ ስለሌለው ቀጥታ ሰውነቱ ላይ በቀረው ፓንት ብቻ ወደአልጋው ሄደ፡፡ ብርድልብሱንና አንሶላውን ገለጠና ከስር ገባ …ወደእሱ ዞረች…ሰውነታቸው ሲነካካ የሁለቱም የሙቀት መጠን ወደላይ ተስፈነጠረ፡፡እሱ ክንዶቹን በአንገቷ ስር ሰቅስቆ አስገባና አቀፋት ..አንገቷን ከትራሱ ላይ ቀና አደረገችና ደረቱ ላይ ተኛች፡፡በአንገቷ ስር የተሻገረው እጁ ተመለሰና በከፊል የተጋለጠው ቀኝ ጡቷ ላይ አረፈ…፡፡ጭንቅላቷ ድረስ ነዘራት፡፡
አካሄዱ ስላላማራት በጥበብ አእምሮውን በመበታተን ልታስቆመው አሰበች..‹‹የእኔ ፍቅር ኑሀሚ እዚህ ከተማ ያለች ይመስልህል?፡፡››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ እዚህ ያለች ይመስለኛል››በእርግጠኝነት መለሰላት፡፡
‹‹ታዲያ ለምን ዛሬውኑ ሳያገናኙን?››
‹‹ያው ምንም ቢሆን እነሱ ባሉት መሰረት ብቻችንን እንደመጣን እስኪያረጋግጡ መሰለኝ››
‹‹እንዴ ምን ነካሽ? በእህታችን ነፍስ እንዴት ቁማር መጫወት እንችላለን…?የአካባቢው መንግስት አቅም ቢኖረው እኮ እስከአሁን ያገኛትና ወደሀገሯ ይመልሳት ነበር፡፡››
‹‹እሱስ እወነትህን ነው..ይሄንን ምናውቀው ግን እኛ ነን..እነሱ የሆነ ነገር ያደርጋሉ ብለው ቢጠረጥሩ ስህተት አልሰሩም፡፡››
‹‹ይሁን እንዳልሽ፡፡እርግጠኛ ነኝ ነገ ብቻችንን መሆናችንን በራሳቸው መንገድ ያረጋግጡና ከእህቴ ያገናኙኛል የሚል እምነት አለኝ››
‹‹አንተ ..››አለችና በድንጋጤ ከደረቱ ላይ ተነሳታ ንግግሯን አራዘመች‹‹ሚስቴ አብራኝ ትመጣለች ብልህ ነግረሀቸዋል እንዴ?››ያላሰበውን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
እሷ ድራማውን በደንብ አድርጋ እየተጫወተችና እነሱ ጋር እንዲደርስላት የምትፈልገውን መልእክት እንዲናግር ሂሳቡን በመስራት ነበር ጥያቄዎችን የምታቀርብለት..እሱ ግን የእሷ ከእሱ ተከትሎ ፔሩ ድረስ መምጣት ከሰዎቹ ጋር ባደረገው በእስከአሁኑ ንግግራቸውም ሆነ ስምምነታቸው ላይ ስላልነበረ..ይሄ በራሱ እንቅፋት እንዳይሆንባቸው ስለፈራ ደነገጠ፡፡
‹‹አንቺ እስከአሁን ማሳወቅ ነበረብኝ…ምን አይነት የማረባ ሰው ነኝ››አለና ከተኛበት በመነሳት አልጋውን ለቆ ወረደ…
‹‹ወደየት ልትሄድ ነው?››
‹‹ነገ ሲመጡ አይተውሽ ሌላ አለመግባባት ውስጥ ከምንገባ አሁኑኑ በኢሜል ላሳውቃቸው፡፡››
ከተኛችበት ሆና ‹‹ጥሩ አስበሀል ማሬ… ፃፈላቸው፡፡››ስትል ፍቃድ ሰጠችው፡፡
እስከአሁን ሳልነግራችሁ የዘነጋሁት አንድ ጉዳይ አለ፡፡ይቅርታ..ባለቤቴ ወደማላውቀው ሀገር ብቻዬን ልትልከኝ ፍቃደኛ ስላልሆነች አብራኝ ተከትላኝ መጥታለች..ቀድሜ ላሳውቃችሁ ብዬ ነው፡፡››
ብሎ ፃፈና ላከው፡፡እና ሞባይሉን ይዞ ወደአልጋው ተመልሶ በመሄድ ከውስጥ ገብቷ ተኛና ምስራቅን መልሶ አቀፎት ለላከው መልዕክት መልስ ይጠብቅ ጀመር፡፡ወዲያው የኢሜሉን መልእክት መልስ መጣለት፡፡
ቀድመህ ልታሳውቀን ይገባ ነበር…ደግመህ ከተስማማንበት ውጭ የሆነ አንዲት ቅንጣት ነገር ብታደርግ እህትህን ማግኘቱን እርሳው፡፡ለጊዜው የሚስትህን መምጣት ተቀብለነዋል፡፡ግን ደግሞ ለአንተ የነገርናቸውን ማስጠንቀቂያዎች እሷም እንድታከብር የማድረግ ኃላፊነቱ ያንተው ነው፡፡
ይላል ፡፡ምስራቅንም አስነበባትና ስልኩን አስቀምጦ መብራቱን አጠፋና አቅፎት ተኛ… ወደጆሮዋ ጠጋ ብሎ በሹክሹክታ‹‹ደህና እደሪ››አላት
‹‹እንቅልፍህ መጣ እንዴ?››
‹‹አይ አልመጣም..የሚመጣም አይመስለኝም..እኚ ሰዎች እስከአሁን ሙሉ በሙሉ ያመኑን አይመስለኝም፣ማለቴ ባልና ሚስት መሆናችንን›› አለችው፡፡
ጆሮዋ ላይ ተለጥፎ‹‹አረ ያምኑናል…እንዲህ እየሆን እንዴት ላያምኑን ይችላሉ? ››
‹‹ባልና ሚስቶች እንዲህ ብቻ አይደለም የሚሆኑት፡፡ይህንን አታውቅም እንዴ? ››
ምን ለማለት እደፈለገች ቢገባውም ያልገባው ለመምሰል ሞከረ ‹‹እንደምታውቂው ከዚህ በፊት አግብቼ አላውቅም… እንዴት ላውቅ እችላለሁ?››
‹‹ለማወቅ እኮ ማግባት አይጠበቅብህም››አለችው በሹክሹክታ
‹‹ታዲያ ምን ይሻለናል እያልሽ ነው?››
‹‹ኑሀሚን አደጋ ላይ የሚጥል ምንም አይነት ስህተት መስራት የለብንም፡፡ አሁን እንተሻሻለን››
..ቀስ ብዬ ልብሴን አወልቅና ወደወለሉ ወረውራለው፡፡ አንትም ፓንትህን ታወልቃለህ ….እኔ ጭን መካከል ትገባለህ..ልክ ወሲብ እንደሚያረግን ባልና ሚስት በንቅናቄና በድምፅ ማስመሰል እንቀጥላለን..ግን በምንም አይነት ሁኔታ እትንህን ጭኔ ውስጥ የእውነት ለመክተት እንዳትሞክር››
‹‹ተንሸራቶ ከገባብኝስ?››
‹‹ወደሀገራችን ስንመለስ ግንባርህን በሽጉጥ አፈርሰውና ባርቆብኝ ነው ብዬ ቃል እሰጣለሁ፡፡››
‹‹ተስማምቼለሁ›› አለና ሙሉ በሙሉ ወደእሷ በመዞር ከሰውነቱ አጣብቆ ያሻት ጀመረ..እሷም ቀስ በቀስ እያደገ እና እየጨመረ በሚሄድ በተቆራረጠ ድምፅ በማጀብ እጆቾን በእርቃን ሰውነቱ ላይ ታመላለስ ጀመር…ድምፃቸው ምን አልባት እየቀረፃቸው ያለው መቅራጫ በጭለማ ምስል ማስቀረት ባይችል እንኳን ወሲብ ላይ መሆናቸውን የሚያበስረውን ድምጽ በትክክል ማስቀረት ስላለበት በደንብ ነበር የተወኑት ፡፡ከ10 ደቂቃ መተሻሸት በኃላ እሷ ቀድማ ከእቅፉ ወጣችና የለበሰችውን ቢጃማ ሆነ ፓንት አወቀለቀችና ወለል ላይ ወረወችው..እሱም ፓንቱን አወለቀና ተመሳሳዩን አደረገ ..ሙሉ በሙሉ እርቃናችውን እርስ በርስ ተጣበቁ ..እሱ ግን የተሰጠውን ትዕዛዝ ማክበር አልቻለም፡፡ከ5 ደቂቃ መፋተግ በኃላ የእሷም ብልት በፈሳሽ መረጣጠቡን ተከትሎ ሙከራው ከሸፈበትና ብልቱ አዳልጦት ከማንነቷ ጋር ሙሉ በሙሉ ተዋሀዳት..ሁለቱም የሆነውን ያወቁት የመጨራሻ ጡዘት ላይ ደርሰው በእርካታ ወደ ስሜታቸው ስክነት ከተመለሱ በኃላ ነው፡፡ምንም አላላች፡፡ከተወሰነ ደቂቃዎች እረፍት በኃላ ሰውነቷ ላይ የነበረውን ብርድልብስ ገፋ አስወገደችና ከአልጋው ወርዳ ወደግድግዳው በመሄድ መብራቱን አበራችው..ይሄንን ሆነ ብላ ነው ያደረገችው..ናኦል ዝርግትግት ብሎ እርቃኑን አልጋው ላይ ተኝቷል ..ቀጥታ ወደሻወር ቤት ሄደች፡፡
ሻወር ቤት ገባችና ውሀውን ከፈተች፡፡ መሀከል አናቷን ማስመታት ጀመረች…አሁን ያደረገችው ነገር ምን እንደሚያመጣባት ምንም እርግጠኛ መሆን አልቻለችም…እሷ በህይወቷ ከመቶ በላይ የማትፈልጋቸውን ወሲባዊ ተራክቦ ከብዙ የማትፈልጋቸው ሰዎች ጋር አድርጋ ታውቃለች፡›ቀድሞውንም አእምሮዋን አሳምና ስለምትከውነው ምንም አይነት የመንፈስ ቁስለት ሆነ ፀፀት አስከትሎባት አያውቅም ነበር፡፡ይሄ የአሁኑ ግን ከአነዛ በጣም የተለየ ነው፡፡ በመጀመሪያ ይሄን ልጅ ገና ከ12 ዓመቱ ጀምሮ ታውቃዋለች፡፡ እያንዳንዱን እንቅስቃሴውን ለውጡን እድገቱን በቅርበት ስትከታተል ነው የኖረችው…ልክ እንደታላቅ እህቱ ስትንከባከበው እና ስትጠብቀው ነው
👍82❤9😁1😱1
የቆየችው…መጀመሪያ ካገኘቻቸው ቀን አንስቶ እህቱን በጣም የምታደንቃት ሲሆን እሱን ደግሞ በጣም ትወደው ነበር፡፡በዚህ የተነሳ እንደቤተሰቦቾ ነው የምታያቸው፡፡ግን አሁን በሆነው ነገር ግራ ተጋባታለች፡፡የእሱ ጥፋት ምንም የለበትም፡፡እንኳን እሱ 30 አመት ያልደፈነ ጎረምሳ ይቅርና የ80 አመት አዛውንትም በዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ገብቶ እራሱን ተቆጣጥሮ ስሜቱን መግታት አይችም..ይሄ ከተፈጥሮ ውጭ ነው፡፡እሷም እራሱ እኮ ስሜቷን መቆጣጠር አልቻለችም፡፡ግን ጉዳዩ ካለቀ በኃለ ልጁ ፍቅር ቢይዘውስ….?ስትል ጠየቀች፡፡ውስጧ ግን እያላት ያለው አንቺ ራስሽ ፍቅር ቢይዝሽስ? ›› ነበር፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
በዛውም list ሊሆን 23ቀን ብቻ የቀረውን Airdrop ላይ ተሳተፉ ብዙ ሰው እየተሳተፈ ነው👇👇👇👇
1 t.me/empirebot/game?startapp=hero405867113
🔥Play with me, grow your startup.
💸 +5k coins as your first gift
💵 +25k coins if you have Telegram Premium
2 https://xn--r1a.website/major/start?startapp=405867113
👑 Join me in @Major game and earn $MAJOR token soon!
⭐️ 750 rating bonus for you.
⭐️ 1000 rating bonus if you are Premium.
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
በዛውም list ሊሆን 23ቀን ብቻ የቀረውን Airdrop ላይ ተሳተፉ ብዙ ሰው እየተሳተፈ ነው👇👇👇👇
1 t.me/empirebot/game?startapp=hero405867113
🔥Play with me, grow your startup.
💸 +5k coins as your first gift
💵 +25k coins if you have Telegram Premium
2 https://xn--r1a.website/major/start?startapp=405867113
👑 Join me in @Major game and earn $MAJOR token soon!
⭐️ 750 rating bonus for you.
⭐️ 1000 rating bonus if you are Premium.
👍52❤10
#ትንሽ_ቦታ…!
በዚህ ዓመት…
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ትንሽ ቦታ መጠለያ
ትንሽ ብቻ መሰደጃ…
ምን-አለበት…?
ለምን-አልባት ብንተውለት…?
ፍጹም መሆን ስለማንችል…
ትንሽ ባዶ እንዋዋል
በልባችን ደግ በኩል
ለአንጎላችን መላወሻ - ትንሽ ቦታ እንተውለት
“ምን-አልባት” የምንልበት…!
ልክ እንደ አምና ለዚህ ዓመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ብንታሰር ይቅር ማያ
ይቅር ብንል መታሰሪያ
ትንሽ እንተው ባዶ ቦታ
ጥግ ድረስ የለም ስራ
ጥግ ድረስ የለም ፋታ
በልባችን ደግ በኩል
እንፈልግ ባዶ ቦታ
የጳጉሜ ዓይነት ትንሽ ቦታ
ለዘመን መለዋወጫ
--------
🔘ነቢይ መኮንን🔘
በዛውም list ሊሆን 23ቀን ብቻ የቀረውን Airdrop ላይ ተሳተፉ ብዙ ሰው እየተሳተፈ ነው👇👇👇👇
t.me/empirebot/game?startapp=hero405867113
🔥Play with me, grow your startup.
💸 +5k coins as your first gift
💵 +25k coins if you have Telegram Premium
በዚህ ዓመት…
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ትንሽ ቦታ መጠለያ
ትንሽ ብቻ መሰደጃ…
ምን-አለበት…?
ለምን-አልባት ብንተውለት…?
ፍጹም መሆን ስለማንችል…
ትንሽ ባዶ እንዋዋል
በልባችን ደግ በኩል
ለአንጎላችን መላወሻ - ትንሽ ቦታ እንተውለት
“ምን-አልባት” የምንልበት…!
ልክ እንደ አምና ለዚህ ዓመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ብንታሰር ይቅር ማያ
ይቅር ብንል መታሰሪያ
ትንሽ እንተው ባዶ ቦታ
ጥግ ድረስ የለም ስራ
ጥግ ድረስ የለም ፋታ
በልባችን ደግ በኩል
እንፈልግ ባዶ ቦታ
የጳጉሜ ዓይነት ትንሽ ቦታ
ለዘመን መለዋወጫ
--------
🔘ነቢይ መኮንን🔘
በዛውም list ሊሆን 23ቀን ብቻ የቀረውን Airdrop ላይ ተሳተፉ ብዙ ሰው እየተሳተፈ ነው👇👇👇👇
t.me/empirebot/game?startapp=hero405867113
🔥Play with me, grow your startup.
💸 +5k coins as your first gift
💵 +25k coins if you have Telegram Premium
👍19❤10
#ኢትዬጵያዊቷ_ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ብራዚል/አማዞን ወንዝ አቅራቢያ
ኑሀሚ በሶስተኛው ቀን የሽሽት ጉዞ በህይወትና በሞት መካከል ሆና የመጨረሻዋን ትንፋሿን ለመሳብ ከፍተኛ ጥረት የምታደርግበት ሁኔታ ላይ ወደቀች፡፡ይሄ የሆነው ድንገት ነው፡፡በብራዚል አማዞኑያ ክልል እየጠለቁ ገብተው የአማዞን ደን እየተሸለከለኩ ሰው ያለበት ቦታ ለመድረስ ጥረት ላይ እያሉ ድንገት የሚያምር ቀይና ውብ አበባ አይታ እሱን ለመቀንጠስ እጇን ስትዘረጋ አበባውን ከያዘው የግንድ ቅርንጫፍ ተለጥፎ ያለ እሾክ ነገር ጠቅ አደረጋት፡፡ትንሽ ነው የደም ጠብታ የታየው፡፡ግን ልብላቤው የተለየ የንብ መነደፍ አይነት ነበር፡፡ግን ደግሞ ብዙም ልታካብድ ስላልፈለገች ለጓደኛዋ እንኳን አልነገረችውም ነበር፡፡ከ10 ደቂቃ በኃላ ግን እግሯ መደናቀፍ ስውነቷ መዛል እና በሙቀት መንደድ ጀመረ…ከዛ በግንባሯ ላብ መንቆርቆር ጀመር…
ካርሎስ ድንገት ወደኃላ እየቀረች ስታስቸግረው ዞር ብሎ ሲያያት በጣም ነው የደነገጠው፡፡
‹‹እንዴ ምን ሆነሻል?››
ለመተንፈስ እንኳን እየተቸገረች..‹‹እኔ እንጃ አራሴን ማንቀሳቀስ እያቃተኝ ነው›››
‹‹ታዲያ አትነግሪኝም እንዴ?››አለና ወደእሷ በመጠጋት ደግፎ ለማረፍ ምቹ ወደሆነ ቦታ ወሰዳት እና ምቹ ቅጠል ጎዝጉዞ አስቀመጣት፡፡
ግንባሯን በእጆቸ እየደበሰ ሙቀቷን መለካት ጀመረ…. ‹‹የወባ መከላከያ አልወሰድሽም እንዴ?››
‹‹አረ ወስ..ጄ..ለሁ››በተቆራረጠ ትንፋሽ መለሰችለት፡፡
ግራ ገባው…‹‹.እስቲ ግንዱን ደገፍ በይ…››አላት፡፡
ደገፍ እንድትል ሲረዳት የቀኝ እጇን የመሀል እጣት ተመለከተ ….ለብቻው ተነርቶ አብጧል፡፡‹‹እንዴ እጣትሽን ምን ሆነሽ ነው?››
እይኗን ወደእጣቷ ወረወረችና አየችው…ደነገጠች‹‹ወይኔ ከደቂቃዎች በፊት እሾክ ወግቶኝ ነበር፤ቀላል አድርጌ ነበር የወሰድኩት፡፡››
አስከአሁን ከደነገጠው በላይ ደነገጠ፡፡ትከሻው ላይ ያለውን ጠመንጃ አወረደና አቀባብሎ ስሯ አስቀምጦ በእጇ አስያዛትና ‹‹የሆነ ነገር ካየሽ ተኩሺ… ስለምሰማ በአስቸኮይ እመጣለሁ…መድሀኒት መፈለግ አለብኝ …. ከዚህ እንዳትንቀሻቀሺ ››አለና፡፡ ጓዙን ጠቅላላ ከጎኗ አስቀምጦ ሽጉጡንና እና ጩቤውን ይዞ ሄደ….ከ15 ደቂቃ አታካች እና አድካሚ ፍለጋ በኃላ ነው የሚፈልገውን ቅጠል ያገኘው፡፡በጥንቃቄ ቆረጠውና ተመልሶ ሲመጣ እሷ ሙሉ በሙሉ እራሷን ስታ ተዘርራ ነበር፡፡
ቶሎ አለና ትንፋሿን አዳመጠ፤በትንሹ ቲር ቲር እያለች በውስጦ ትንፈራገጣለች፡፡ እጇን አነሳና ጉልበቱ ላይ አስተካከሎ አስቀመጣት፡፡ወገቡ ላይ የሻጠውን ጩቤ ከጎኑ አወጣና የተመረዘውን የመሀል እጣቷን ሸረከተው፤ጥቁር ደም ከውስጡ መንፎልፎል ጀመረ፡፡ይበቃል በሚለው መጠን ካፈሰሰ በኃላ የጨቀጨቀውን ቅጠል እየጨመቀ ፈሳሹን ወደውስጥ ያንጠባጥብ ጀመረ፡፡ከዛ ሙሉ የእጇን መዳፍ ውጩንም ውስጥንም በቅጠሉ ጠቀለለውና ከስር የለበሰውን ካኔቴራ አውልቆ በመቀዳደድ ልክ እንደፋሻ ጠቀለለውና በቀስታ አስተካክሎ ሰውነቷ ላይ አስቀመጠው፡፡ እሷን ፎጣ ነገር አልብሶት ወደቦታዋ መልሶ አስተኛትና ውጤቱን መጠበቅ ጀመረ…በጣም ተጨንቋል፡፡ይህቺን ልጅ በዚህ ደን ውስጥ ካጣት ከዛ በኃላ ያለው ህይወት እንዴት ሊቀጥል እንደሚችልም ምንም አያውቅም…ከሳምንት በፊት ያወቃት ሳይሆን እድሜ ልክ በልቡም በነፍስም የነበረች ሴት እንደሆነች ነው እያሰበ ያለው፡፡አሁን እጁ ላይ ከሞተችበት ልቡም ሆነች ነፍሱ ከዚህ በፊት ቦዳ ከሆነችው በላይ በጥልቀት ባዶ ትሆናለች፡፡ለመኖር ወኔም ፍላጎትም አይኖረውም፡፡በዚህ እርግጠኛ ስለሆነ ውስጡን በረደው፡፡
ስለእሷ እያሰበ የእሷን መንቃት እየተጠባበቀ ሳለ የሆነ ጆሮው ላይ ሿሿሿ የሚል ድምጽ ሰማ…ይሄ ድምፅ የወንዝ መስገምገም ድምፅ እንደሆነ ያውቃል፡፡ጆሮውን በደንብ ቀስሮና ስሜቱን ሰብስቦ እርግጠኛ ለመሆን አዳመጠ፤ትክክል ነው….ተነሳ ቆመ፡፡ የእሷን ቦርሳም ሆነ እሱ ይዞ የነበረውን ሻንጣ ውስጥ ከተተ፡፡ ሽጉጡንም ከተተና በተከሻው አዘለው…ከዛ ጎንበስ አለና እሷን ልክ እንደተወዳጅ ልጁ በጥንቃቄ ከስር ሰቅስቆ ያዛትና አቅፎ ወደላይ አነሳት፡፡የገመተውን ያህል አልከበደችውም….‹‹ድሮስ በፍቅር የተሸከሙት ሸክም የክብደቱን ያህል መች ይፈተናል?››አለና በውስጡ አሰበ ፡፡እሷን ተሸክሞ ከሀረጋ ሀረጎች እና ከጥሻዎች ጋር እየታገለ ለ15 ደቂቃ ወንዙ ሿሿሿታ ወደሚሰማበት አቅጣጫ ይዞት ተጎዛ፡፡ የሚንፎለፎለው ወንዝ የአይኖቹ እይታ ውስጥ ሲገብ ውስጡ በእርካታ ሀሴት አደረጋች፡፡ወደወንዙ ዳርቻ ተጠጋና ምቹ ያለውን ቦታ መርጦ ቀስ ብሎ ተንበረከከና አስቀመጣት ››ወዲያው ደህና ደህና ችካል መሰል እንጨቶችን መርጦ ጉድጎድ በመቆፈር አስተካክሎ ተከላቸው፡፡በአግዳሚ ማገር አራቱንም ኮርነር አገናኛና አርብራብ ሰራላቸው…እዛ እርብራብ ላይ ምቹና ለስላሳ ቅጠል ለምልሞ ጎዘጎዘበት፡፡በመቀጠል ረጃጅም ቋሚዎቹን ቆራረጠና አራት ቦታ ተክሎ ልክ እንደጎጆ ቤት ከላይ ጫፋቸውን አንድ ላይ ሰበሰባና በሀረግ አሰራቸው፡፡ከዛ እንደክብ ዙሪያውን እያሽከረከረ አሰረና አጠናካረው.፡፡ከዛ ኮባ መሳይ ሰፊ ቅጠሎችን በመመልመል አለበሰውና በግማሽ ቀን ውስጥ የሚያምር ጊዜያው ጎጆ ሰራ፡፡ከዛ ኑሀሚን ከመሬት ላይ አንስቶ በጥንቃቄ ወደጎጆው አስገባትና ያዘጋጀላት ርብራብ ላይ አስተኛት፡፡ይሄ ሁሉ ሲሆን ግን ኑሀሚ ከገባችበት ሰመመን አልነቃችም..ጥሩ ነገር ግን ሙቀቷ በመጠኑ ቀንሶ አተነፋፋሶም እየተስተካከለ መጥቶ የሰላም እንቅልፍ የተኛች መስላለች፡፡ስለዚህ ሰውነቷ ለመድሀኒቱ ለመልስ እየሰጠና በሰውነቷ የገባው መርዝ እየተዳከመ እና እየተወገደ እንደሆነ ስላመነ ተረጋግቷል፡፡
ልብሱን አወላልቆ ወደወንዙ ውስጥ ገባና እየዋኘ በዛውም አራት የሚሆኑ አሳዎችን አሰገረና ከወንዙ ወጥቶ ልብሱን በመለባበስ ወደሰራት ጎጆ ተመልሶ እንጨት እርስ በርስ በማፋተግ እሳት አቀጣጥሎ ዓሳውን መጥበስ ጀመረ፡፡ልክ የመጀመሪያውን ዓሳ አብስሎ ጨርሶ ሁለተኛውን እያዘጋጀ ሳለ ኑሀሚ አይኖቾን ገለጠች፡፡ብዣ እንዳለባት ነው፡፡ሞት ጫፍ ላይ ደርሶ መመለስ አይነት ስሜት እየተሰማት ነው፡፡ዙሪያውን ስትቃኝ ጥቅጥቅ የአማዞን ድን ሳይሆን አዲስ የተሰራ የገጠር ጎጆ ቤት ነው የሚታያት፡፡አይኖቾን ስታሽከከረክር በጎጆዋ በራፍ አሻግራ ስታይ ሰማያዊ የጠራ መልክ ያለው ወራጅ ወንዝ ይታያታል..ከወንዙ ማዶ ግን መልሶ በግዙፍ ዕድሜ ጠገብ ዛፎች የተዋቀረ ጥቅጥቅ ደን ነው የምታያት…እይታዋን ወዳለችበት ስታጠብ ጭስ ነገር አየች…ቀስቀስ ስትል ድምፅ ስለሰማ የያዘውን ነገር ጣጣለና ተፈናጥሮ ተነስቶ ስሯ ቆመ….‹‹ነቃሽ…?እንዴት ነሽ ..?አሁን ምን ይሰማሻል?››በጥያቄ አጣደፋት፡፡
‹‹በጣም ደህና ነኝ..ፍፁም ሰላም ነው እየተሰማኝ ያለው…እንዴት እዚህ መጣን …?የሆነ ዛፍ ስራ አልነበርኩ..?ወንዙ ከየት መጣ?፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ…በአካባቢው ወንዝ እንዳለ ሳውቅ ወደእዚህ ይዤሽ መጣሁና ይህቺን ጎጆ ሰራሁ..አሁን ቆንጆ የዓሳ ጥብስ ሰራቼለው፡፡እሱን ስትበይ ደግሞ ጠንካራ ትሆኚያለሽ››
‹‹ይዤሽ መጣሁ ስትል..እንዴት አድርገህ…?መቼስ በእግሬ መንቀሳቀስ አልችልም ነበር..አይደል እንዴ?››
‹‹ያው አቀፍኩሽና አመጣሁሽ..እሩቅ እኮ አይደለም..አንድ ሶስት ኪሎ ሜትር ቢርቅ ነው፡፡››
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ብራዚል/አማዞን ወንዝ አቅራቢያ
ኑሀሚ በሶስተኛው ቀን የሽሽት ጉዞ በህይወትና በሞት መካከል ሆና የመጨረሻዋን ትንፋሿን ለመሳብ ከፍተኛ ጥረት የምታደርግበት ሁኔታ ላይ ወደቀች፡፡ይሄ የሆነው ድንገት ነው፡፡በብራዚል አማዞኑያ ክልል እየጠለቁ ገብተው የአማዞን ደን እየተሸለከለኩ ሰው ያለበት ቦታ ለመድረስ ጥረት ላይ እያሉ ድንገት የሚያምር ቀይና ውብ አበባ አይታ እሱን ለመቀንጠስ እጇን ስትዘረጋ አበባውን ከያዘው የግንድ ቅርንጫፍ ተለጥፎ ያለ እሾክ ነገር ጠቅ አደረጋት፡፡ትንሽ ነው የደም ጠብታ የታየው፡፡ግን ልብላቤው የተለየ የንብ መነደፍ አይነት ነበር፡፡ግን ደግሞ ብዙም ልታካብድ ስላልፈለገች ለጓደኛዋ እንኳን አልነገረችውም ነበር፡፡ከ10 ደቂቃ በኃላ ግን እግሯ መደናቀፍ ስውነቷ መዛል እና በሙቀት መንደድ ጀመረ…ከዛ በግንባሯ ላብ መንቆርቆር ጀመር…
ካርሎስ ድንገት ወደኃላ እየቀረች ስታስቸግረው ዞር ብሎ ሲያያት በጣም ነው የደነገጠው፡፡
‹‹እንዴ ምን ሆነሻል?››
ለመተንፈስ እንኳን እየተቸገረች..‹‹እኔ እንጃ አራሴን ማንቀሳቀስ እያቃተኝ ነው›››
‹‹ታዲያ አትነግሪኝም እንዴ?››አለና ወደእሷ በመጠጋት ደግፎ ለማረፍ ምቹ ወደሆነ ቦታ ወሰዳት እና ምቹ ቅጠል ጎዝጉዞ አስቀመጣት፡፡
ግንባሯን በእጆቸ እየደበሰ ሙቀቷን መለካት ጀመረ…. ‹‹የወባ መከላከያ አልወሰድሽም እንዴ?››
‹‹አረ ወስ..ጄ..ለሁ››በተቆራረጠ ትንፋሽ መለሰችለት፡፡
ግራ ገባው…‹‹.እስቲ ግንዱን ደገፍ በይ…››አላት፡፡
ደገፍ እንድትል ሲረዳት የቀኝ እጇን የመሀል እጣት ተመለከተ ….ለብቻው ተነርቶ አብጧል፡፡‹‹እንዴ እጣትሽን ምን ሆነሽ ነው?››
እይኗን ወደእጣቷ ወረወረችና አየችው…ደነገጠች‹‹ወይኔ ከደቂቃዎች በፊት እሾክ ወግቶኝ ነበር፤ቀላል አድርጌ ነበር የወሰድኩት፡፡››
አስከአሁን ከደነገጠው በላይ ደነገጠ፡፡ትከሻው ላይ ያለውን ጠመንጃ አወረደና አቀባብሎ ስሯ አስቀምጦ በእጇ አስያዛትና ‹‹የሆነ ነገር ካየሽ ተኩሺ… ስለምሰማ በአስቸኮይ እመጣለሁ…መድሀኒት መፈለግ አለብኝ …. ከዚህ እንዳትንቀሻቀሺ ››አለና፡፡ ጓዙን ጠቅላላ ከጎኗ አስቀምጦ ሽጉጡንና እና ጩቤውን ይዞ ሄደ….ከ15 ደቂቃ አታካች እና አድካሚ ፍለጋ በኃላ ነው የሚፈልገውን ቅጠል ያገኘው፡፡በጥንቃቄ ቆረጠውና ተመልሶ ሲመጣ እሷ ሙሉ በሙሉ እራሷን ስታ ተዘርራ ነበር፡፡
ቶሎ አለና ትንፋሿን አዳመጠ፤በትንሹ ቲር ቲር እያለች በውስጦ ትንፈራገጣለች፡፡ እጇን አነሳና ጉልበቱ ላይ አስተካከሎ አስቀመጣት፡፡ወገቡ ላይ የሻጠውን ጩቤ ከጎኑ አወጣና የተመረዘውን የመሀል እጣቷን ሸረከተው፤ጥቁር ደም ከውስጡ መንፎልፎል ጀመረ፡፡ይበቃል በሚለው መጠን ካፈሰሰ በኃላ የጨቀጨቀውን ቅጠል እየጨመቀ ፈሳሹን ወደውስጥ ያንጠባጥብ ጀመረ፡፡ከዛ ሙሉ የእጇን መዳፍ ውጩንም ውስጥንም በቅጠሉ ጠቀለለውና ከስር የለበሰውን ካኔቴራ አውልቆ በመቀዳደድ ልክ እንደፋሻ ጠቀለለውና በቀስታ አስተካክሎ ሰውነቷ ላይ አስቀመጠው፡፡ እሷን ፎጣ ነገር አልብሶት ወደቦታዋ መልሶ አስተኛትና ውጤቱን መጠበቅ ጀመረ…በጣም ተጨንቋል፡፡ይህቺን ልጅ በዚህ ደን ውስጥ ካጣት ከዛ በኃላ ያለው ህይወት እንዴት ሊቀጥል እንደሚችልም ምንም አያውቅም…ከሳምንት በፊት ያወቃት ሳይሆን እድሜ ልክ በልቡም በነፍስም የነበረች ሴት እንደሆነች ነው እያሰበ ያለው፡፡አሁን እጁ ላይ ከሞተችበት ልቡም ሆነች ነፍሱ ከዚህ በፊት ቦዳ ከሆነችው በላይ በጥልቀት ባዶ ትሆናለች፡፡ለመኖር ወኔም ፍላጎትም አይኖረውም፡፡በዚህ እርግጠኛ ስለሆነ ውስጡን በረደው፡፡
ስለእሷ እያሰበ የእሷን መንቃት እየተጠባበቀ ሳለ የሆነ ጆሮው ላይ ሿሿሿ የሚል ድምጽ ሰማ…ይሄ ድምፅ የወንዝ መስገምገም ድምፅ እንደሆነ ያውቃል፡፡ጆሮውን በደንብ ቀስሮና ስሜቱን ሰብስቦ እርግጠኛ ለመሆን አዳመጠ፤ትክክል ነው….ተነሳ ቆመ፡፡ የእሷን ቦርሳም ሆነ እሱ ይዞ የነበረውን ሻንጣ ውስጥ ከተተ፡፡ ሽጉጡንም ከተተና በተከሻው አዘለው…ከዛ ጎንበስ አለና እሷን ልክ እንደተወዳጅ ልጁ በጥንቃቄ ከስር ሰቅስቆ ያዛትና አቅፎ ወደላይ አነሳት፡፡የገመተውን ያህል አልከበደችውም….‹‹ድሮስ በፍቅር የተሸከሙት ሸክም የክብደቱን ያህል መች ይፈተናል?››አለና በውስጡ አሰበ ፡፡እሷን ተሸክሞ ከሀረጋ ሀረጎች እና ከጥሻዎች ጋር እየታገለ ለ15 ደቂቃ ወንዙ ሿሿሿታ ወደሚሰማበት አቅጣጫ ይዞት ተጎዛ፡፡ የሚንፎለፎለው ወንዝ የአይኖቹ እይታ ውስጥ ሲገብ ውስጡ በእርካታ ሀሴት አደረጋች፡፡ወደወንዙ ዳርቻ ተጠጋና ምቹ ያለውን ቦታ መርጦ ቀስ ብሎ ተንበረከከና አስቀመጣት ››ወዲያው ደህና ደህና ችካል መሰል እንጨቶችን መርጦ ጉድጎድ በመቆፈር አስተካክሎ ተከላቸው፡፡በአግዳሚ ማገር አራቱንም ኮርነር አገናኛና አርብራብ ሰራላቸው…እዛ እርብራብ ላይ ምቹና ለስላሳ ቅጠል ለምልሞ ጎዘጎዘበት፡፡በመቀጠል ረጃጅም ቋሚዎቹን ቆራረጠና አራት ቦታ ተክሎ ልክ እንደጎጆ ቤት ከላይ ጫፋቸውን አንድ ላይ ሰበሰባና በሀረግ አሰራቸው፡፡ከዛ እንደክብ ዙሪያውን እያሽከረከረ አሰረና አጠናካረው.፡፡ከዛ ኮባ መሳይ ሰፊ ቅጠሎችን በመመልመል አለበሰውና በግማሽ ቀን ውስጥ የሚያምር ጊዜያው ጎጆ ሰራ፡፡ከዛ ኑሀሚን ከመሬት ላይ አንስቶ በጥንቃቄ ወደጎጆው አስገባትና ያዘጋጀላት ርብራብ ላይ አስተኛት፡፡ይሄ ሁሉ ሲሆን ግን ኑሀሚ ከገባችበት ሰመመን አልነቃችም..ጥሩ ነገር ግን ሙቀቷ በመጠኑ ቀንሶ አተነፋፋሶም እየተስተካከለ መጥቶ የሰላም እንቅልፍ የተኛች መስላለች፡፡ስለዚህ ሰውነቷ ለመድሀኒቱ ለመልስ እየሰጠና በሰውነቷ የገባው መርዝ እየተዳከመ እና እየተወገደ እንደሆነ ስላመነ ተረጋግቷል፡፡
ልብሱን አወላልቆ ወደወንዙ ውስጥ ገባና እየዋኘ በዛውም አራት የሚሆኑ አሳዎችን አሰገረና ከወንዙ ወጥቶ ልብሱን በመለባበስ ወደሰራት ጎጆ ተመልሶ እንጨት እርስ በርስ በማፋተግ እሳት አቀጣጥሎ ዓሳውን መጥበስ ጀመረ፡፡ልክ የመጀመሪያውን ዓሳ አብስሎ ጨርሶ ሁለተኛውን እያዘጋጀ ሳለ ኑሀሚ አይኖቾን ገለጠች፡፡ብዣ እንዳለባት ነው፡፡ሞት ጫፍ ላይ ደርሶ መመለስ አይነት ስሜት እየተሰማት ነው፡፡ዙሪያውን ስትቃኝ ጥቅጥቅ የአማዞን ድን ሳይሆን አዲስ የተሰራ የገጠር ጎጆ ቤት ነው የሚታያት፡፡አይኖቾን ስታሽከከረክር በጎጆዋ በራፍ አሻግራ ስታይ ሰማያዊ የጠራ መልክ ያለው ወራጅ ወንዝ ይታያታል..ከወንዙ ማዶ ግን መልሶ በግዙፍ ዕድሜ ጠገብ ዛፎች የተዋቀረ ጥቅጥቅ ደን ነው የምታያት…እይታዋን ወዳለችበት ስታጠብ ጭስ ነገር አየች…ቀስቀስ ስትል ድምፅ ስለሰማ የያዘውን ነገር ጣጣለና ተፈናጥሮ ተነስቶ ስሯ ቆመ….‹‹ነቃሽ…?እንዴት ነሽ ..?አሁን ምን ይሰማሻል?››በጥያቄ አጣደፋት፡፡
‹‹በጣም ደህና ነኝ..ፍፁም ሰላም ነው እየተሰማኝ ያለው…እንዴት እዚህ መጣን …?የሆነ ዛፍ ስራ አልነበርኩ..?ወንዙ ከየት መጣ?፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ…በአካባቢው ወንዝ እንዳለ ሳውቅ ወደእዚህ ይዤሽ መጣሁና ይህቺን ጎጆ ሰራሁ..አሁን ቆንጆ የዓሳ ጥብስ ሰራቼለው፡፡እሱን ስትበይ ደግሞ ጠንካራ ትሆኚያለሽ››
‹‹ይዤሽ መጣሁ ስትል..እንዴት አድርገህ…?መቼስ በእግሬ መንቀሳቀስ አልችልም ነበር..አይደል እንዴ?››
‹‹ያው አቀፍኩሽና አመጣሁሽ..እሩቅ እኮ አይደለም..አንድ ሶስት ኪሎ ሜትር ቢርቅ ነው፡፡››
👍72❤8🥰8👏2
ውስጧ ተንቦጫቦጨ እና ዝም አለች፡፡እሱ ወደስራው ተመለሰና እየጠበሰ ያለውና ዓሳ አገላበጠ ፡፡ ቀድሞ ጠብሶ ያስቀመጠውን ዓሳ ይዞ ወደ እሷ ተጠጋ የሰራው የእንጨት አልጋ ርብርብ ጠርዝ ላይ ቁጨ አለና ከዓሳው እየቆረሰ እሾኩን በጥንቃቄ ከስጋው እየለየ ያጎርሳት ጀመር፡፡በዝግታና በዝምታ ትጎርስ ጀመር፡፡ይሄ በክፉ ቀኗ በክፉ ሁኔታ ላይ ያገኘችው የበአድ ሀገር ሰው እያደረገላት ያለው እንክብካቤ እና እያሳያት ያለው ፍቅር በህይወቷ ከወንድሟ ውጭ ካለ ሌላ ሰው አግኝታው የማታውቀው ነበርና እጅግ ስሜታዊ አደረጋትና ሳታስበው እንባዋ በጉንጮቾ እየተንከባለለ መርገፍ ጀመር፡፡
‹‹ምን ሆንሽ ..?አመመሽ እንዴ?››ደነገጠ፡፡
‹‹አይ..ደስ ብሎኝ ነው…ህይወቴን ብዙ ጊዜ ደጋግመህ አድነሀታል…እድሜ ልኬን ከፍዬ የማልጨርሰው ውላታ አለብኝ …..እንዴት አድርጌ እንደምከፍልህ አላውቅም…››አለችው፡፡
‹‹ካሰብሽበት ቀላል ነው››አላት
‹‹ምን ንገረኝ….?አደረገዋለው››
‹‹አገርሽ ይዘሺኝ ትሄጂና ታገቢኛለሽ፡፡››
ድንግጥ..አለች…አይኖቾ.ፈጠጡ፡፡
‹‹አረ ተረጋጊ ..ስቀልድ ነው..አትደንግጪ››
‹‹አይ አልደነገጥኩም››
‹‹እሱማ በደንብ ደንግጠሸል..ግን የትኛው ነው ያስደነገጠሸ?››
‹‹ከምንና ከምኑ?››
‹‹ማለቴ ወደሀገር ውሰጂኝ ያልኩሽ ነው ወይስ አግቢኝ ያልኩሽ?››
‹‹ሁለቱም አላስደነገጡኝም..ያው ቀልድህን እንደሆነ አውቃለው…ይሄንን ከመሰለ የምድር ገነት የሆነ ሀገር ለቀህ ውቅያኖስ ሰንጥቀህ አህጉር አቋርጠህ ኢትዬጵያ ድረስ ትሄዳለህ?››
‹‹ካንቺ ጋር ከሆነ አትጠራጠሪ…ይህቺ ኢትዬጵያ የምትባለው ሀገር አንቺን የመሰለች ጠይም መልአክ ማብቀል ከቻለች ምድሯም ለምለም አየሯም ማራኪ እንደሚሆን ጥርጥር የለኝም፡፡››
‹‹እርሱስ ትክክል ነህ …እናንት የአለም ጉዙፍ ወንዝ ቢኖራችሁም እኛ ደግሞ የአለም ረጅሞ ወንዝ የአባይ ባለቤት ነን፡፡በተፈጥሮ ሀብት በኩልም ደኑ ብትል፤ ተራራው፤ ሀይቁ ብትል፤ወንዙ፤ በረሀው ብትል፤ እሳተ ጎመራው…የባዬ ደይቨርሲቲ ሀብታም ሀገር ነች፡፡እንደ እናንተ ቡና የኢኮኖሚ ምንጫችን ነው፡፡እንደእናንተ በኳስ ተጫዋቾች ባንታደልም..በኳስ ደጋፊነት እና ተንታኝነት ከእናንተ አንተናነስም፡፡››
‹‹በገለፃሽ እኮ ይበልጥ እያበረታታሺኝና እያስጎመዠሽኝ ነው፡፡››
‹‹እስኪ መጀመሪያ ከእዚህ ደን በህይወት እንውጣና የዛን ጊዜ ሀሳብህን የማትቀይር ከሆነ እና ይህንን ጥያቄ ደግመህ የምታቀርብልኝ ከሆነ በሁኔታው ላይ ደግመን እናየዋለን፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
በዛውም list ሊሆን 22 ቀን ብቻ የቀረውን Airdrop ላይ ተሳተፉ ብዙ ሰው እየተሳተፈ ነው👇👇👇👇
1 t.me/empirebot/game?startapp=hero405867113
🔥Play with me, grow your startup.
💸 +5k coins as your first gift
💵 +25k coins if you have Telegram Premium
‹‹ምን ሆንሽ ..?አመመሽ እንዴ?››ደነገጠ፡፡
‹‹አይ..ደስ ብሎኝ ነው…ህይወቴን ብዙ ጊዜ ደጋግመህ አድነሀታል…እድሜ ልኬን ከፍዬ የማልጨርሰው ውላታ አለብኝ …..እንዴት አድርጌ እንደምከፍልህ አላውቅም…››አለችው፡፡
‹‹ካሰብሽበት ቀላል ነው››አላት
‹‹ምን ንገረኝ….?አደረገዋለው››
‹‹አገርሽ ይዘሺኝ ትሄጂና ታገቢኛለሽ፡፡››
ድንግጥ..አለች…አይኖቾ.ፈጠጡ፡፡
‹‹አረ ተረጋጊ ..ስቀልድ ነው..አትደንግጪ››
‹‹አይ አልደነገጥኩም››
‹‹እሱማ በደንብ ደንግጠሸል..ግን የትኛው ነው ያስደነገጠሸ?››
‹‹ከምንና ከምኑ?››
‹‹ማለቴ ወደሀገር ውሰጂኝ ያልኩሽ ነው ወይስ አግቢኝ ያልኩሽ?››
‹‹ሁለቱም አላስደነገጡኝም..ያው ቀልድህን እንደሆነ አውቃለው…ይሄንን ከመሰለ የምድር ገነት የሆነ ሀገር ለቀህ ውቅያኖስ ሰንጥቀህ አህጉር አቋርጠህ ኢትዬጵያ ድረስ ትሄዳለህ?››
‹‹ካንቺ ጋር ከሆነ አትጠራጠሪ…ይህቺ ኢትዬጵያ የምትባለው ሀገር አንቺን የመሰለች ጠይም መልአክ ማብቀል ከቻለች ምድሯም ለምለም አየሯም ማራኪ እንደሚሆን ጥርጥር የለኝም፡፡››
‹‹እርሱስ ትክክል ነህ …እናንት የአለም ጉዙፍ ወንዝ ቢኖራችሁም እኛ ደግሞ የአለም ረጅሞ ወንዝ የአባይ ባለቤት ነን፡፡በተፈጥሮ ሀብት በኩልም ደኑ ብትል፤ ተራራው፤ ሀይቁ ብትል፤ወንዙ፤ በረሀው ብትል፤ እሳተ ጎመራው…የባዬ ደይቨርሲቲ ሀብታም ሀገር ነች፡፡እንደ እናንተ ቡና የኢኮኖሚ ምንጫችን ነው፡፡እንደእናንተ በኳስ ተጫዋቾች ባንታደልም..በኳስ ደጋፊነት እና ተንታኝነት ከእናንተ አንተናነስም፡፡››
‹‹በገለፃሽ እኮ ይበልጥ እያበረታታሺኝና እያስጎመዠሽኝ ነው፡፡››
‹‹እስኪ መጀመሪያ ከእዚህ ደን በህይወት እንውጣና የዛን ጊዜ ሀሳብህን የማትቀይር ከሆነ እና ይህንን ጥያቄ ደግመህ የምታቀርብልኝ ከሆነ በሁኔታው ላይ ደግመን እናየዋለን፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
በዛውም list ሊሆን 22 ቀን ብቻ የቀረውን Airdrop ላይ ተሳተፉ ብዙ ሰው እየተሳተፈ ነው👇👇👇👇
1 t.me/empirebot/game?startapp=hero405867113
🔥Play with me, grow your startup.
💸 +5k coins as your first gift
💵 +25k coins if you have Telegram Premium
👍79❤20🥰9👏3🎉2🔥1
ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
ልጅም ቶሎ ያንጠለጠለውን የእጅ ቦርሳ ጠረጴዛ ላይ አደረገና ከብር የተሠራ የሚመስል ሁለት የእጅ ብራስሌት መጀመሪያ ምስራቅ እጅ ላይ ቀጥሎ ናኦል እጅ ላይ አጠለቀና ከኪሱ ስልኩን አውጥቶ በማብራት ሲነካካ እጃቸው ላይ ያጠለቀላቸው ብራስሌት ቀለሙን ከብራማነት ወደ ደማቅ ሰማያዊነት ቀየረ።ዝም ብሎ ሁኔታውን ሲከታተል የነበረው ዳግላስ መናገር ጀመረ
"አሁን እንግደህ እህታችሁን እኔ ሳልሆን ለእናንተ ማመጣላችሁ ..እናንተ ናችሁ ለእኔ የምታመጡልኝ..." ብሎ ኑሀሚ የእሱን ሰው ገድላ ከሌላ ከእሱ ሰው ጋር እንደኮበለለች...እስከአሁንም በመላው አማዞን ደን ውስጥ ቢያስፈልጋት ሊያገኛት እንዳልቻለ...እሷን መሞቷን ካላረጋገጠ ወይም በህይወት እጅ ካላስገባት የሰላም እንቅልፍ እንደማይወስደው..ወንድሟን ያስመጣበት ምክንያት ተሳክቶላት እንኳን ማምለጥ ብትችል ለወንድሟ ደህንነት ስትል በፍቃዷ መልሳ እጅ እንድትሰጥ አቅዶ ያደረገው እንደሆነ አብራርቶ ከአሁን ሰዓት በኃላ እዛው እሱ የሚኖርበት ወለል ላይ የራሳቸው ክፍል እንደሚሰጣቸው እና እጃቸው ላይ በተጠለቀላቸው አንባር ሙሉ የ24 ሰዓት ክትትል እንደሚደረግላቸው ነገራቸው። እሷ መጥታ በፍቃዷ እጇን እስክትሰጥ ወይንም መሞቷ እስኪረጋገጥ ድረስ ከክፍላቸው መውጣት እንደማይችሉ...ፀባያቸውን እስካሳመሩና ችግር ለመፍጠር እስካልሞከሩ ድረስ የሚፈልጉት ነገር እንደሚያሟላላቸው አብራርቶላቸው.. ወደክፍላቸው እንዲወስዳቸው አዘዘ...።የታዘዘውም ታጣቂ እየጎተ ወሰዶ አንድ ለቀቅ ያለ ሻወርና ማንበቢያ ክፍል ያለው ባለአንድ ክፍል ቤት ውስጥ አስገብቶ ከውጭ ዘጋባቸው..
እቤት ውስጥ ከገብ በኃላ እንኳን ናኦል እና ምስራቅ ለረጅም ደቂቃ ደንዝዘውና ፈዘው ማህል ወለል ላይ በዝምታ ተገትረው ነበር።
ናኦል እንባ እየተናነቀው"ምስራቅ ምን ውስጥ ነው የገባነው..?ይሄ ሰውዬ ተጫወተብን"አላት ።
ምስራቅም ወደእሱ ተንደረደረችና አቀፈችው ።አንገቱ ስር ሽጉጥ ብላ በጆሮው "አትደንግጥ...እቅድ አለኝ"አለችው።
ዝም አለ...ከዚህ ለመውጣት ምን አይነት ተአምራዊ ዕቅድ ሊኖራት እንደሚችል ምንም ሊገለፅለት አልቻለም።ቢሆንም ከሞስራቅ ጋር ባሳለፋቸው በርካታ አመታት ብዙ ተአምር መሳይ ነገሮችን ስትከውንና ደጋግሞም ሲሳካላት ታዝቦልና የተናገረችው ነገር ንቆ ሊያልፈው አልደፈረም።...
ብራዚል/አማዞን ደን ውስጥ
አካባቢው ድቅድቅ ጨለማ ነው፡፡ጨረቃዋም በሰማይ ላይ ብርሀን አልፈነጠቀችም፡፡ከዋክብቱም የከሰሙ መስለዋል ፡፡ኑሀሚ ካርሎስ የሰራላት የአንጨት ርብራብ አልጋ ላይ ተኝታ የእጇ ጥዝጣዜ ታዳምጣለች፡፡እርግጥ ከትናንቱ የተሻ ጤንነት ላይ ብትገኝም ሰውነቷ ግን ሙሉ በሙሉ እደዛለ ነው፡፡በህይወቷ በእንዲህ አይነት ደካማንትና አቅመ ቢስነት ተሰምቷት አያውቅም፡፡ ካርሎስ በሶስት ቀን ውስጥ ሙሉ በሙሉ እደምታገግም ነግሯት ነበር ፡፡ አሁን አሁን ያለችበት ሁኔታ ስታስበው በሶስት ወር ተሽሏት ከዚህ አካባቢ የምትንቀሳቀስ እየመሰላት አይደለም፡፡ያም ሆኖ ግን ትናንትና ጉሮሮዋን ፈጥርቆ ነፍሷን ሊነጥቃት የነበረው ሲኦላዊ ህመም ዛሬ በሙሉ አቅሙ የለም፡፡ያ የሆነው ደግሞ ካርሎስ እጇ ላይ ባሰረለት የባህል መድሀኒት ምክንያት ነው፡፡
እንደምንም አንገቷን ወደ ዳር ሸርተት አድርጋ አየችው፡፡ እዛው ርብራብ አልጋ ጎን ባለ ጠፍጣፍ ድንጋይ ላይ ተቀምጦ አንገቱን በካኔቴራው ሙሉ በሙሉ ሸፍኖ የእንጨት አልጋውን ቋሚ ተደግፎ ጨልጥ ያለ እንቅልፍ ተኝቷል፡፡ አሳዘናት፡፡ቢቻላት ኩርምት ብሎ በተቀመጠበት እንቅልፍ የወሰደውን ይሄን መልካም ሰው ጎትታ ወደራሷ ስባ እሷ የተኛችበት የእንጨት ርብራብ ላይ ከጎኗ ሽጉጥ አድርጋው ብትተኛ ደስ ይላት ነበር ፡፡
ወዲያው ሀሳቧን ሳትጨርስ ነጎድጓድ በሰማዩ አንፀባራቂ ብርሀን እየረጨ ያንቧርቅ ጀመር፡፡የሚያስፈራ ደራጎናዊ ድምፅ አካባቢውን ያናጋው ጀመር፡፡ ኑሀሚ እንኳን በእንደዚህ አይነት ሁኔታ እንደዚህ አይነት ቦታ ሆና ይቅርና በሀገሯ ሰማይ ስር በገዛ ቤቷ እያለች ሳይቀር እንዲህ አይነት ነጎድጎድ በጣም ነው የሚያስፈራት፡፡፡እንደምንም ደካማ እጃን አንቀሳቀሰችና ትከሻው ላይ አኑራ በመወዝወዝ..‹‹ካርሎስ ካርሎስ›› ስትል ጠራችው፡፡
በርግጎ ተነሳ‹‹..ምን …አመመሽ እንዴ?››
‹‹አይ ነጎድጎድ ፈራለሁ››
ከተቀመጠበት ተነሳና ወደእሷ ተንቀሳቀሰ….ርብራቡ ጠርዝ ላይ ከጎኗ ተቀመጠና እጆቿን በእጆቹ ውስጥ አስገብቶ ያሻሽላት ጀመር፡፡ከእሱ ሰውነት ወደእሷ እየተላለፈ ያለው ሙቀት ብቻ ሳይሆን ብርታትና ጥንካሬ ጭምር ነው፡፡
በድጋሚ‹‹በጣም እኮ ነው የፈረሁት››አለችው፡፡
‹‹አይዞሽ…ስጋታችን፤ፍረሀቶችንና እና ጥርጣሬዎቻችን ሰው በመሆናችን የተሰጡን ፀጋዎች ናቸው፡፡ካለበለዚያማ እህያና በቅሎ መሰል አይነት ስሜቶች ስለሌላቸው ከእኛ የተሻሉ እደለኞች ናቸው ልንል መሆኑ ነው?፡፡››
‹‹እሱስ እውትህን ነው››አለችና ይበልጥ ተለጠፈችበት
ወዲያው ሰማዩን አግቶ ይዞ የነበረውን ዝናብ ዘረገፈው፡፡የተሰራችው ጊዜያዊ ጎጆ ሙሉ በሙሉ በዛ ድቅድቅ ጨለማ የሚወርደውን የዝናብ ውሀ አግዳ ለማስቀረት ጥንካሬው አልነበራትም፡፡ሁለቱም በ5 ደቂቃ ውስጥ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በዝናብ ራሱ፡፡እሷ ከህመሙና የሰውነት ጥንካሬዋ በመዳከሙ የተነሳ ዝናቡንና ቅዝቃዜውን መቋቋም ስላልቻለች ትዘፈዘፈች፣ካርሎስ የሚያደርገው ጠፋበት፡፡ ሙሉ በሙሉ ወደእንጨት አልጋው ወጣና ከእሷ ተስተካክሎ ተኛ…አቀፋትና ወደራሱ አስጠግቶ ከሰውነቱ ለጠፋት፡፡የናፈቀውን የእናቱን ጡት እንዳገኘ ህፃን ልጥፍ አለችበት፡፡የተሻለ ምቾት ተሰማት፡፡ከዝናብ ውርጅብኝ የምትሸሸግበት መጠለያ ዋሻ ያገኘች አይነት ስሜት ተሰማት፡፡ እጆቹን በረጠበ ልብሷ ስር ሰቅስቆ በማስገባት ሰውነቷን ላይ አሳረፈና ይዳብሳት ጀመር..፡፡ከዛ ቀስ እያለ ከንፈሩን ከንፋሯ ላይ አሳረፈና በቀስታ ይመጣት ጀመር፡፡አሁን ከውስጧ እየተቀጣጠለ ያለው ሙቀት ወደላይኛው የሰውነት ቆዳ በመድረስ ከላይ የሚያርፋባትን ዝናብ የሚያስከትልባትን ቅዝቃዜ እያተነ የሚያስወግድላት እየመሰላት ነው፡፡ጭልጥ ያለ ምናባዊ ህልም ውስጥ ነው የገባችው፡፡ከንፈራቸው ሳይላቀቅ ዝናቡም ከመቆሙ በፊት እሷ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰዳት፡፡
ስትነቃ ጎጆዋ በጥዋት የደመቀ የፀሀይ ፈንጣቂ አድምቋታል፡፡ሁሉ ነገር ብሩህ ፣ ሁሉ ነገር ዳማቅ ሆኖ ነው እየታየ ያለው፡፡እራሷን ለማንቀሳቀስ ሞከረች፡፡ አሁንም ሰውነቷ እንደተሳሰረ ነው፡፡ወደ ጎን አንገቷን መልሳ ተመለከተች፡፡ ለሊት ጎኗ ተኝቶ የነበረው ጉብል አሁን የለም፡፡አይኖቾን ብታንከራትትም ጎጆው ባዶ ነው፡፡ አንደምንም እራሷን አበረታታ ከተኛችበት ተነሳች፡፡ ዱላ መሰል እንጨት ተደግፋ እንደምንም እግሮቾን እየጎተተች ወደጎጆዋ በራፍ ሄደች፡፡ፊት ለፊቷ ያለው አማዞን ወንዝ እየተገማሸረ ጥሩ አቋም ላይ አንዳለ የማራቶን ራጭ ወደፊት እየገሰገሰ ነው፡፡አካባቢውን የሞሉት ውብና ማራኪ ወፎች ወዲህና ወዲያ አክሮባት እየሰሩ ይዝናናሉ.. አይኖቾን አሩቅ ስታማትር ካርሎስ በ500 ሜትር ርቀት በፓንት ብቻ አማዞን ወንዝ ውስጥ ጠልቆ ገብቶ ዓሳ ላመስገረ ሲዳክር ተመከተችው፡፡ፈገግ አለችና ወደ ውስጥ ተመለሰች፡፡ወደ ሻንጣቸው ተጠጋች ፡፡ውሀ የማያሳገባውን የሻንጣ ዚፕ ከፍታ ውስጥ ያለውን የካርሎስን ማስታወሻ ደብተር ከእነእስኪሪብቶው አወጣች፡፡እዛው መሬት ይዛ ተቀመጠችና ለመፅሀፍ ተዘጋጀች፡፡
( በአመዞን ደን ውስጥ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፡
፡
ልጅም ቶሎ ያንጠለጠለውን የእጅ ቦርሳ ጠረጴዛ ላይ አደረገና ከብር የተሠራ የሚመስል ሁለት የእጅ ብራስሌት መጀመሪያ ምስራቅ እጅ ላይ ቀጥሎ ናኦል እጅ ላይ አጠለቀና ከኪሱ ስልኩን አውጥቶ በማብራት ሲነካካ እጃቸው ላይ ያጠለቀላቸው ብራስሌት ቀለሙን ከብራማነት ወደ ደማቅ ሰማያዊነት ቀየረ።ዝም ብሎ ሁኔታውን ሲከታተል የነበረው ዳግላስ መናገር ጀመረ
"አሁን እንግደህ እህታችሁን እኔ ሳልሆን ለእናንተ ማመጣላችሁ ..እናንተ ናችሁ ለእኔ የምታመጡልኝ..." ብሎ ኑሀሚ የእሱን ሰው ገድላ ከሌላ ከእሱ ሰው ጋር እንደኮበለለች...እስከአሁንም በመላው አማዞን ደን ውስጥ ቢያስፈልጋት ሊያገኛት እንዳልቻለ...እሷን መሞቷን ካላረጋገጠ ወይም በህይወት እጅ ካላስገባት የሰላም እንቅልፍ እንደማይወስደው..ወንድሟን ያስመጣበት ምክንያት ተሳክቶላት እንኳን ማምለጥ ብትችል ለወንድሟ ደህንነት ስትል በፍቃዷ መልሳ እጅ እንድትሰጥ አቅዶ ያደረገው እንደሆነ አብራርቶ ከአሁን ሰዓት በኃላ እዛው እሱ የሚኖርበት ወለል ላይ የራሳቸው ክፍል እንደሚሰጣቸው እና እጃቸው ላይ በተጠለቀላቸው አንባር ሙሉ የ24 ሰዓት ክትትል እንደሚደረግላቸው ነገራቸው። እሷ መጥታ በፍቃዷ እጇን እስክትሰጥ ወይንም መሞቷ እስኪረጋገጥ ድረስ ከክፍላቸው መውጣት እንደማይችሉ...ፀባያቸውን እስካሳመሩና ችግር ለመፍጠር እስካልሞከሩ ድረስ የሚፈልጉት ነገር እንደሚያሟላላቸው አብራርቶላቸው.. ወደክፍላቸው እንዲወስዳቸው አዘዘ...።የታዘዘውም ታጣቂ እየጎተ ወሰዶ አንድ ለቀቅ ያለ ሻወርና ማንበቢያ ክፍል ያለው ባለአንድ ክፍል ቤት ውስጥ አስገብቶ ከውጭ ዘጋባቸው..
እቤት ውስጥ ከገብ በኃላ እንኳን ናኦል እና ምስራቅ ለረጅም ደቂቃ ደንዝዘውና ፈዘው ማህል ወለል ላይ በዝምታ ተገትረው ነበር።
ናኦል እንባ እየተናነቀው"ምስራቅ ምን ውስጥ ነው የገባነው..?ይሄ ሰውዬ ተጫወተብን"አላት ።
ምስራቅም ወደእሱ ተንደረደረችና አቀፈችው ።አንገቱ ስር ሽጉጥ ብላ በጆሮው "አትደንግጥ...እቅድ አለኝ"አለችው።
ዝም አለ...ከዚህ ለመውጣት ምን አይነት ተአምራዊ ዕቅድ ሊኖራት እንደሚችል ምንም ሊገለፅለት አልቻለም።ቢሆንም ከሞስራቅ ጋር ባሳለፋቸው በርካታ አመታት ብዙ ተአምር መሳይ ነገሮችን ስትከውንና ደጋግሞም ሲሳካላት ታዝቦልና የተናገረችው ነገር ንቆ ሊያልፈው አልደፈረም።...
ብራዚል/አማዞን ደን ውስጥ
አካባቢው ድቅድቅ ጨለማ ነው፡፡ጨረቃዋም በሰማይ ላይ ብርሀን አልፈነጠቀችም፡፡ከዋክብቱም የከሰሙ መስለዋል ፡፡ኑሀሚ ካርሎስ የሰራላት የአንጨት ርብራብ አልጋ ላይ ተኝታ የእጇ ጥዝጣዜ ታዳምጣለች፡፡እርግጥ ከትናንቱ የተሻ ጤንነት ላይ ብትገኝም ሰውነቷ ግን ሙሉ በሙሉ እደዛለ ነው፡፡በህይወቷ በእንዲህ አይነት ደካማንትና አቅመ ቢስነት ተሰምቷት አያውቅም፡፡ ካርሎስ በሶስት ቀን ውስጥ ሙሉ በሙሉ እደምታገግም ነግሯት ነበር ፡፡ አሁን አሁን ያለችበት ሁኔታ ስታስበው በሶስት ወር ተሽሏት ከዚህ አካባቢ የምትንቀሳቀስ እየመሰላት አይደለም፡፡ያም ሆኖ ግን ትናንትና ጉሮሮዋን ፈጥርቆ ነፍሷን ሊነጥቃት የነበረው ሲኦላዊ ህመም ዛሬ በሙሉ አቅሙ የለም፡፡ያ የሆነው ደግሞ ካርሎስ እጇ ላይ ባሰረለት የባህል መድሀኒት ምክንያት ነው፡፡
እንደምንም አንገቷን ወደ ዳር ሸርተት አድርጋ አየችው፡፡ እዛው ርብራብ አልጋ ጎን ባለ ጠፍጣፍ ድንጋይ ላይ ተቀምጦ አንገቱን በካኔቴራው ሙሉ በሙሉ ሸፍኖ የእንጨት አልጋውን ቋሚ ተደግፎ ጨልጥ ያለ እንቅልፍ ተኝቷል፡፡ አሳዘናት፡፡ቢቻላት ኩርምት ብሎ በተቀመጠበት እንቅልፍ የወሰደውን ይሄን መልካም ሰው ጎትታ ወደራሷ ስባ እሷ የተኛችበት የእንጨት ርብራብ ላይ ከጎኗ ሽጉጥ አድርጋው ብትተኛ ደስ ይላት ነበር ፡፡
ወዲያው ሀሳቧን ሳትጨርስ ነጎድጓድ በሰማዩ አንፀባራቂ ብርሀን እየረጨ ያንቧርቅ ጀመር፡፡የሚያስፈራ ደራጎናዊ ድምፅ አካባቢውን ያናጋው ጀመር፡፡ ኑሀሚ እንኳን በእንደዚህ አይነት ሁኔታ እንደዚህ አይነት ቦታ ሆና ይቅርና በሀገሯ ሰማይ ስር በገዛ ቤቷ እያለች ሳይቀር እንዲህ አይነት ነጎድጎድ በጣም ነው የሚያስፈራት፡፡፡እንደምንም ደካማ እጃን አንቀሳቀሰችና ትከሻው ላይ አኑራ በመወዝወዝ..‹‹ካርሎስ ካርሎስ›› ስትል ጠራችው፡፡
በርግጎ ተነሳ‹‹..ምን …አመመሽ እንዴ?››
‹‹አይ ነጎድጎድ ፈራለሁ››
ከተቀመጠበት ተነሳና ወደእሷ ተንቀሳቀሰ….ርብራቡ ጠርዝ ላይ ከጎኗ ተቀመጠና እጆቿን በእጆቹ ውስጥ አስገብቶ ያሻሽላት ጀመር፡፡ከእሱ ሰውነት ወደእሷ እየተላለፈ ያለው ሙቀት ብቻ ሳይሆን ብርታትና ጥንካሬ ጭምር ነው፡፡
በድጋሚ‹‹በጣም እኮ ነው የፈረሁት››አለችው፡፡
‹‹አይዞሽ…ስጋታችን፤ፍረሀቶችንና እና ጥርጣሬዎቻችን ሰው በመሆናችን የተሰጡን ፀጋዎች ናቸው፡፡ካለበለዚያማ እህያና በቅሎ መሰል አይነት ስሜቶች ስለሌላቸው ከእኛ የተሻሉ እደለኞች ናቸው ልንል መሆኑ ነው?፡፡››
‹‹እሱስ እውትህን ነው››አለችና ይበልጥ ተለጠፈችበት
ወዲያው ሰማዩን አግቶ ይዞ የነበረውን ዝናብ ዘረገፈው፡፡የተሰራችው ጊዜያዊ ጎጆ ሙሉ በሙሉ በዛ ድቅድቅ ጨለማ የሚወርደውን የዝናብ ውሀ አግዳ ለማስቀረት ጥንካሬው አልነበራትም፡፡ሁለቱም በ5 ደቂቃ ውስጥ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በዝናብ ራሱ፡፡እሷ ከህመሙና የሰውነት ጥንካሬዋ በመዳከሙ የተነሳ ዝናቡንና ቅዝቃዜውን መቋቋም ስላልቻለች ትዘፈዘፈች፣ካርሎስ የሚያደርገው ጠፋበት፡፡ ሙሉ በሙሉ ወደእንጨት አልጋው ወጣና ከእሷ ተስተካክሎ ተኛ…አቀፋትና ወደራሱ አስጠግቶ ከሰውነቱ ለጠፋት፡፡የናፈቀውን የእናቱን ጡት እንዳገኘ ህፃን ልጥፍ አለችበት፡፡የተሻለ ምቾት ተሰማት፡፡ከዝናብ ውርጅብኝ የምትሸሸግበት መጠለያ ዋሻ ያገኘች አይነት ስሜት ተሰማት፡፡ እጆቹን በረጠበ ልብሷ ስር ሰቅስቆ በማስገባት ሰውነቷን ላይ አሳረፈና ይዳብሳት ጀመር..፡፡ከዛ ቀስ እያለ ከንፈሩን ከንፋሯ ላይ አሳረፈና በቀስታ ይመጣት ጀመር፡፡አሁን ከውስጧ እየተቀጣጠለ ያለው ሙቀት ወደላይኛው የሰውነት ቆዳ በመድረስ ከላይ የሚያርፋባትን ዝናብ የሚያስከትልባትን ቅዝቃዜ እያተነ የሚያስወግድላት እየመሰላት ነው፡፡ጭልጥ ያለ ምናባዊ ህልም ውስጥ ነው የገባችው፡፡ከንፈራቸው ሳይላቀቅ ዝናቡም ከመቆሙ በፊት እሷ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰዳት፡፡
ስትነቃ ጎጆዋ በጥዋት የደመቀ የፀሀይ ፈንጣቂ አድምቋታል፡፡ሁሉ ነገር ብሩህ ፣ ሁሉ ነገር ዳማቅ ሆኖ ነው እየታየ ያለው፡፡እራሷን ለማንቀሳቀስ ሞከረች፡፡ አሁንም ሰውነቷ እንደተሳሰረ ነው፡፡ወደ ጎን አንገቷን መልሳ ተመለከተች፡፡ ለሊት ጎኗ ተኝቶ የነበረው ጉብል አሁን የለም፡፡አይኖቾን ብታንከራትትም ጎጆው ባዶ ነው፡፡ አንደምንም እራሷን አበረታታ ከተኛችበት ተነሳች፡፡ ዱላ መሰል እንጨት ተደግፋ እንደምንም እግሮቾን እየጎተተች ወደጎጆዋ በራፍ ሄደች፡፡ፊት ለፊቷ ያለው አማዞን ወንዝ እየተገማሸረ ጥሩ አቋም ላይ አንዳለ የማራቶን ራጭ ወደፊት እየገሰገሰ ነው፡፡አካባቢውን የሞሉት ውብና ማራኪ ወፎች ወዲህና ወዲያ አክሮባት እየሰሩ ይዝናናሉ.. አይኖቾን አሩቅ ስታማትር ካርሎስ በ500 ሜትር ርቀት በፓንት ብቻ አማዞን ወንዝ ውስጥ ጠልቆ ገብቶ ዓሳ ላመስገረ ሲዳክር ተመከተችው፡፡ፈገግ አለችና ወደ ውስጥ ተመለሰች፡፡ወደ ሻንጣቸው ተጠጋች ፡፡ውሀ የማያሳገባውን የሻንጣ ዚፕ ከፍታ ውስጥ ያለውን የካርሎስን ማስታወሻ ደብተር ከእነእስኪሪብቶው አወጣች፡፡እዛው መሬት ይዛ ተቀመጠችና ለመፅሀፍ ተዘጋጀች፡፡
👍86❤7👎1😁1
ሀሳቧ ለወንድሞ ደብዳቤ ለመፅሀፍ ነው፡፡ለሊት እንዛ በአየሩ ነጎድጓድ ሲረጭ… ከሰማይ ዶፍ ዝናብ ሲወርድ… በውስጧ በተፈጠረባት ፍራቻ ድንገት ብሞትስ? ወንድሜ የሆነ ነገር ሳልለው እንዴት ይሆናል? ብላ አሰበችና በሰላም ለሊቱ ነግቶ ለጥዋት ፀሀይ ከበቃች ለወንድሟ ደብዳቤ ጻፋ እንደምታስቀምጥ ለራሷ ቃል ገባች፡፡ድንገት ብትሞት ካርሎስ ደብዳቤውን ለወንድሞ አንደሚያደርስላት እርግጠኛ ነች፡፡ ደብዳውን መፃፍ ጀመረች፡፡
ወንድሜ-
…የእኔ ትዝታ
ደህና ሁን
….. ቀንና ማታ
ትዝ ይልሀል ይሄን ዘፈን እየደጋገምኩ ስዘፍንልህ? በጣም እኮ ነው የምወድህ...ገና እናታችን ማህፀን ውስጥ ሆነን እንኳን ምርጥ ጎደኛዬ ነበርክ..እና እዛም ሆነን በጣም ነበር የምወድህ...ከተወለድን በኃላም የእናታችንን ግራና ቀኝ ጡት ተካፍለን አይን ለአይን እየተያየን በፍቅር ስንጠባ ሁሉ እወድህ ነበር...ወላጆቻችን ሞተው ቤታችን ሁሉ በለቀስተኞች ተሞልቶ ዋይ ዋይ በሚባልበት በዛን ወቅት እናትና አባቱን አጥቶ ወንድሜ እንዴት ይቋቋመዋል?ብዬ አጨነቅ ነበር...ግን እኮ የሞቱት የእኔም ወላጆች ነበሩ፤የተጎዳሁት እኔም ነኝ...ግን ደግሞ ከእኔ በላይ አንተ ታሳዝነኝ ነበር።ጎዳና ተጥለን ስንኖርም የእኔ ረሀብ ሳይሆን ያንተ ሆድ መንጓጓት ነበር የሚያሳምመኝ።ብቻ ገና ከፅንሰታችን ጀምሮ እስከዚህች ሰዓት ድረስ አንተ ብቸኛ ወንድሜ ነህ...አንተ ብቸኛ የልብ ጓደኛዬ ነህ...አንተ ብቸኛ ዘመዴና የልቤም የነፍሴም ሰው ነህ።
ወንድምአለም ለስራ በመጣሁበት የሠው ሀገር አንድ ትዝታውን ተነጥቆ አእምሮው የተናጋበትን ሰው በሰባአዊነት ረዳለሁ ብዬ የማልወጣበት ቅርቃር ውስጥ ገብቻለሁ።ሠውን ለመርዳት ሲሉ ችግር ውስጥ መግባት እኮ የአንተ እንጂ የእኔ ባህሪ አልነበረም።ግን ያው ሰው ነኝና አንዳንዴ ስህተት እሰራለሁ… እናም … በቀላሉ የማይታረም ስህተት ሰራሁ።ልረዳው ያልኩት ሰው ኮኬይን አምራች አለምአቀፍ ሽብርተኛ ሆኖ ተገኘ።እኔንም አፍነው አማዞን ማህፀን ውስጥ ጣሉኝ፡፡ ላንተ ለወንድሜ ለመትረፍ ስል ብዙ ታገልኩ፤ሊቀብሩኝ ከቆፈሩት ጉድጓድ ሌላ ሰው ገድዬ በመቅበር ለማምለጥ ሞክሬ ነበር።ከዛ እንደውቅያኖስ ዝርግ እንደሸረሪት ድር የተጠማዘዘና የተወሳሰበ ከሆነው ደን በቀላሉ ወጥቶ የአንተ የወንድሜን አይን ለማየት መቻል ቀላል ሆኖ አላገኘሁትም።ካርሎስ በሚባል አንድ ቀና ሰው ድጋፍ ለማምለጥ ባደረኩት ጥረት ከአጋቾቼ እገታ የራቅኩ ቢሆንም በአጋጣሚ በአንድ መርፌ መሠል እሾህ እጣቴን ተወግቼ ተመርዤለሁ...እርግጥ ይሄ ካርሎስ የተባለው መልካምና ተወዳጅ ሰው ከጫካው ባህላዊ መድሀኒት ፈልጎ አክሞኛል … ፍፅሞ እስከወዲያኛው በመዳኔ እርግጠኛ ባልሆንም የተወሰነ ለውጥ ግን እያየሁ ነው፡፡
አንድ ሩሲያ የስለላ ስልጣና ስወስድ መምህሬ የነበረ ሰው ‹‹በጉዞህ ተስፋ አትቁረጥ...ይሄ የሚሆነው ግን ነገሮች በትንሹም ቢሆን እያደጉና እየተሻሻሉ ከሄድ ብቻ ነው።ነገሮች ባሉበት የቆሙ ከሆነ ወይም እድገታቸው የኃሊት ከሆነ በጊዜ ተስፋ መቁረጥ እና አቅጣጫን ማስተካከል የብልህ ውሳኔ ነው።››ይል ነበር፡፡
ምን አልባት መርዙ ቀድሞ ሰውነቴን የመረዘው መሠለኝ።እና ምን አልባት ወደነእማዬ የመሄጂያ ቀኔ የደረሠ ይመስለኛል።እና እንደዛ ከሆነ መጠንከር አለብህ።አታየኝም ብለህ ብትዝረከረክና እራስህን ብትጥል በጣም ነው ሚደብረኝ።
ይበልጥ ጠንካራና ትልቅ ሰው መሆን አለብህ።ቸኮሌት ፍብሪካው ሲያልቅ ሁሌ በየአመቱ በልደት ቀኔ አንድ ሶስት ካርቶን ለህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ ላሉ ህፃናት በእኔ ስም ትሰጥልኛለህ።እነሱ ደስ ሲላቸው እያየሁ እኔም ደስ ይለኛል።
ምስራቅን ቸው በልልኝ።ወንድሜን አደራ ብሎሻል በልልኝ።በጣም ነው የምወድህ የእኔ ወንድም።፡፡
ፅፋ ስትጨርስ ወረቀቱን አጣጠፈችና ከጀርባው የወንድሟን ሙሉ አድራሻ ከነስልክ ቁጥሩ ፅፍበት አጣጥፍ አስቀመጠች።
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
በዛውም list ሊሆን 19 ቀን ብቻ የቀረውን Airdrop ላይ ተሳተፉ ብዙ ሰው እየተሳተፈ ነው👇👇👇👇
t.me/empirebot/game?startapp=hero405867113
🔥Play with me, grow your startup.
💸 +5k coins as your first gift
💵 +25k coins if you have Telegram Premium
ወንድሜ-
…የእኔ ትዝታ
ደህና ሁን
….. ቀንና ማታ
ትዝ ይልሀል ይሄን ዘፈን እየደጋገምኩ ስዘፍንልህ? በጣም እኮ ነው የምወድህ...ገና እናታችን ማህፀን ውስጥ ሆነን እንኳን ምርጥ ጎደኛዬ ነበርክ..እና እዛም ሆነን በጣም ነበር የምወድህ...ከተወለድን በኃላም የእናታችንን ግራና ቀኝ ጡት ተካፍለን አይን ለአይን እየተያየን በፍቅር ስንጠባ ሁሉ እወድህ ነበር...ወላጆቻችን ሞተው ቤታችን ሁሉ በለቀስተኞች ተሞልቶ ዋይ ዋይ በሚባልበት በዛን ወቅት እናትና አባቱን አጥቶ ወንድሜ እንዴት ይቋቋመዋል?ብዬ አጨነቅ ነበር...ግን እኮ የሞቱት የእኔም ወላጆች ነበሩ፤የተጎዳሁት እኔም ነኝ...ግን ደግሞ ከእኔ በላይ አንተ ታሳዝነኝ ነበር።ጎዳና ተጥለን ስንኖርም የእኔ ረሀብ ሳይሆን ያንተ ሆድ መንጓጓት ነበር የሚያሳምመኝ።ብቻ ገና ከፅንሰታችን ጀምሮ እስከዚህች ሰዓት ድረስ አንተ ብቸኛ ወንድሜ ነህ...አንተ ብቸኛ የልብ ጓደኛዬ ነህ...አንተ ብቸኛ ዘመዴና የልቤም የነፍሴም ሰው ነህ።
ወንድምአለም ለስራ በመጣሁበት የሠው ሀገር አንድ ትዝታውን ተነጥቆ አእምሮው የተናጋበትን ሰው በሰባአዊነት ረዳለሁ ብዬ የማልወጣበት ቅርቃር ውስጥ ገብቻለሁ።ሠውን ለመርዳት ሲሉ ችግር ውስጥ መግባት እኮ የአንተ እንጂ የእኔ ባህሪ አልነበረም።ግን ያው ሰው ነኝና አንዳንዴ ስህተት እሰራለሁ… እናም … በቀላሉ የማይታረም ስህተት ሰራሁ።ልረዳው ያልኩት ሰው ኮኬይን አምራች አለምአቀፍ ሽብርተኛ ሆኖ ተገኘ።እኔንም አፍነው አማዞን ማህፀን ውስጥ ጣሉኝ፡፡ ላንተ ለወንድሜ ለመትረፍ ስል ብዙ ታገልኩ፤ሊቀብሩኝ ከቆፈሩት ጉድጓድ ሌላ ሰው ገድዬ በመቅበር ለማምለጥ ሞክሬ ነበር።ከዛ እንደውቅያኖስ ዝርግ እንደሸረሪት ድር የተጠማዘዘና የተወሳሰበ ከሆነው ደን በቀላሉ ወጥቶ የአንተ የወንድሜን አይን ለማየት መቻል ቀላል ሆኖ አላገኘሁትም።ካርሎስ በሚባል አንድ ቀና ሰው ድጋፍ ለማምለጥ ባደረኩት ጥረት ከአጋቾቼ እገታ የራቅኩ ቢሆንም በአጋጣሚ በአንድ መርፌ መሠል እሾህ እጣቴን ተወግቼ ተመርዤለሁ...እርግጥ ይሄ ካርሎስ የተባለው መልካምና ተወዳጅ ሰው ከጫካው ባህላዊ መድሀኒት ፈልጎ አክሞኛል … ፍፅሞ እስከወዲያኛው በመዳኔ እርግጠኛ ባልሆንም የተወሰነ ለውጥ ግን እያየሁ ነው፡፡
አንድ ሩሲያ የስለላ ስልጣና ስወስድ መምህሬ የነበረ ሰው ‹‹በጉዞህ ተስፋ አትቁረጥ...ይሄ የሚሆነው ግን ነገሮች በትንሹም ቢሆን እያደጉና እየተሻሻሉ ከሄድ ብቻ ነው።ነገሮች ባሉበት የቆሙ ከሆነ ወይም እድገታቸው የኃሊት ከሆነ በጊዜ ተስፋ መቁረጥ እና አቅጣጫን ማስተካከል የብልህ ውሳኔ ነው።››ይል ነበር፡፡
ምን አልባት መርዙ ቀድሞ ሰውነቴን የመረዘው መሠለኝ።እና ምን አልባት ወደነእማዬ የመሄጂያ ቀኔ የደረሠ ይመስለኛል።እና እንደዛ ከሆነ መጠንከር አለብህ።አታየኝም ብለህ ብትዝረከረክና እራስህን ብትጥል በጣም ነው ሚደብረኝ።
ይበልጥ ጠንካራና ትልቅ ሰው መሆን አለብህ።ቸኮሌት ፍብሪካው ሲያልቅ ሁሌ በየአመቱ በልደት ቀኔ አንድ ሶስት ካርቶን ለህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ ላሉ ህፃናት በእኔ ስም ትሰጥልኛለህ።እነሱ ደስ ሲላቸው እያየሁ እኔም ደስ ይለኛል።
ምስራቅን ቸው በልልኝ።ወንድሜን አደራ ብሎሻል በልልኝ።በጣም ነው የምወድህ የእኔ ወንድም።፡፡
ፅፋ ስትጨርስ ወረቀቱን አጣጠፈችና ከጀርባው የወንድሟን ሙሉ አድራሻ ከነስልክ ቁጥሩ ፅፍበት አጣጥፍ አስቀመጠች።
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
በዛውም list ሊሆን 19 ቀን ብቻ የቀረውን Airdrop ላይ ተሳተፉ ብዙ ሰው እየተሳተፈ ነው👇👇👇👇
t.me/empirebot/game?startapp=hero405867113
🔥Play with me, grow your startup.
💸 +5k coins as your first gift
💵 +25k coins if you have Telegram Premium
❤52👍47😢5👏3
🌼ውድ የቻናሉ ተከታዎችእንኳን ለ 2017 ዓ.ም አዲስ ዓመት በሠላም በጤና አደረሳችሁ
❤️በዓሉ የሠላም፣ የጤና፣ የደስታ እና የፍቅር አመት እንዲሆን ለሁላችሁም ረጅም እድሜን ከጤና ጋር እንመኛለን !
🌼መልካም አዲስ ዓመት ለሁላችን🌼
@atronosee
❤️በዓሉ የሠላም፣ የጤና፣ የደስታ እና የፍቅር አመት እንዲሆን ለሁላችሁም ረጅም እድሜን ከጤና ጋር እንመኛለን !
🌼መልካም አዲስ ዓመት ለሁላችን🌼
@atronosee
👍9❤4