አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
572 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ፍቅር_ከፈላስፋ


#ክፍል_ሀያ_አምስት



ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ



❤️ፌናን
===
‹‹….ምን አልባት ትክክል ነሽ››አለኝ
‹‹ምኑን አባ…?››
‹‹እውነቱን የማወቅ መብት አለሽ …እናም ነገርሻለው››
አቀማመጤን አስተካከልኩ..በስካርና በድካም እየታጠፉ የነበሩ ጆሮዎቼን ሲነቃቁና ሲዘረጋጉ ይታወቀኛል…
‹‹በዚህ የታፈነ በምትይው የእኔ እና የእናትሽ ኑሮ ውስጥ ባጣም ተጎጂው እኔ ሳልሆን እናትሽ ነች››
‹‹ማለት…?››
‹‹የመፋታቱን ሀሳብ አንቺ ከመወለደሽም በፊት ሆነ ከተወለድሽ በኃላ ደጋግሜ አቅርቤላት ነበር::ግን ከተለየዋት እራሷን እንድምታጠፋ ደጋግማ ስላስጠነቀቀቺኝ ነው ጥያቄዬን አቁሜ ሀሳቤንም ቀይሬ ዝም ብዬ እንደምታይው መኖር የጀምርኩት..››
‹‹መኖራችሁ ካልቀረ ታዲያ እንደ ሰዎቹ በስርዓት አትኖሩም..…?እንደባልና ሚስት››
‹‹እንደዛ መኖር አንችልም..ታሪኩን ከመጀመሪያ ላስረዳሽ…እናትሽ የአዲስአባ ልጅ ብትሆንም የእናቷ ቤተሰቦች የአንቦ ኦሮሞዎች እንደሆኑ ታውቂያለሽ››የሚናገርውን ነገር ማስረዳት ስለከበደው ዙሪያ ጥምዝ እንደሚሽከረከር ገባኝ ..አሁን እያለኝ ያለው እኮ ያንቺ ሰም መቼስ ፌናን እንደሆነ ታውቂያለሽ አይደል …?ቢጤ ነው፡፡
‹‹…..እና ልክ እኔ እና እናትሽ እንደተጋባን ሰሞን የእናቷ ታናሽ ወንድም ስሙ ቶሌራ ይባላል ..በውድቅት ለሊት በራፋችንን አንኳክቶ ይመጣል….ሲመጣ ሰው አይመስልም…ልብሱ በጭቃና በከሰል ብናኝ በክቷ፤በደረቀ ደም ተለውሶ ነበር…ማንነቱን በመልኩ ሳይሆን በድምጹ ነበር እናትሽ የለየችው…ከዛ አፋፍሰን ወደቤት አስገብተን ሰውነቱን እንዲታጠብ አድርገን ልብሱን ቀይረን የቆሰለውን የተቻለንን ያህል የመጀመሪያ እርዳታ እንዲያገኝ አድርገን አስተኛነው…
‹‹ምን ሆኖ ነበር…?››
ይሄ ልጅ ብሩህ ጭንቅት ያለው ድንቅ ልጅ ነበር…ግን ያው እንደማንኛውም የዘመኑ ወጣት ፓለቲካ ውስጥ እስከአንገቱ ነበር የገባበት::እኔም ሆንኩ እናትሽ እንደው ባጋጣሚ ወይ እኛ ሄደን ወይ ደግሞ እሱ ሊጠይቃና በመጣ ቁጥር ነገሮችን በእርጋታ እንዲይዛቸው ልንመክረው ሞክረን ነበር::አዎ ያቅማችንን ጥረን ነበር:: ግን ያው ታውቂያለሽ አንዳንዴ ፓለቲካ ልክ እንደልክፍት ነው::ሰው ተይ ባለሽ ቁጥር ይበለጥ ይብስብሻል..እና ይሄ የማታውቂው አጎትሽ ሚስጥራዊ የኦነግ አባል ሆኖ በአንቦ ከታማ ይንቀሳቀስ ነበር::.እና ህዝቡን ያነሳሱና መንግስትን በመቃወም ከተማዋን ያምሶታል ::በዛም ምክንያት ብዙ የመንግስትና የግል ንብረት ይወድማል::ከወታደሩም ከኑዋሪውም ከ12 ሰዋች በላይ ይሞታሉ…እና የዚህ ጉዳይ መሪ ይሄ አጎትሽ እንደሆነ በከተማዋ የሚንቀሳቀሱ ደህነነቶች መረጃ ይደርሳቸውና ለሊቱን አድፍጠው ሊይዙት ወደቤት ሄደው ሲከቡት አንዱን ገድሎ ሁለቱን አቁስሎ አጥር ዘሎ ያመልጣል፡፡እድል ከእሱ ጋር ነበረችና ከሰል በጫነ መኪና መሀል በድብቅ ተወሽቆ በለሊት አዲስአበባ ይገባና እንደነገርኩሽ በውድቅት ለሊት ወደእኛ ቤት ይመጣል፡፡
‹‹ታዲያ እንዲት አደረጋችሁ…?››ጥያቄዬን ቀጠልኩ..እኔ መስማት ከምፈልገው የወላጆቼ የጋብቻ ታሪክ ውጭ የሆነ ሀገራዊ እና ፓለቲካዊ ታሪክ ለምን እንደሚነግረኝ ፍንጩን እንኳን ማወቅ አቅቶኝ ፡፡
‹‹ለጊዜው ምን አልባት የእኛ ቤት አስታማማኝ ላይሆን ስለሚችል እና በጥቆማ መጥተው ቢፈትሹ ሊያገኙት ስለሚችሉ ብለን ሊነጋጋ ሲል አቃቂ የሚኖር አንድ ጎደኛዬ ቤት ወስደን አስተኛነውና እዛው ህክምና እንዲያገኝ አድርገን በዘላቂነት ምን ማድረግ እንዳለብን ማሰብ ጀመርን::እናትሽ ለእሱ ያላት ፍቅር ይሄን ያህል ነው ተብሎ ከሚለካው በላይ ነበር…‹አይኔ እያየ አይገሉብኝም ወይም አስርቤት አይጥሉብኝም ብላ በድብቅ ከሀገር ይዛው ልትስወጣው ተነሳች…ቢያንስ እስከድንበር ልትሸኘው::ስሰማ ተቃወምኩ….የተቃወምኩት ለማድረግ ያሰበቸው ነገር አግባብ አይደለም ብዬ አይደለም..ለእሱ ያላትን ፍቅር ስለማውቅ ከዛ በላይም ላድርግለት ብትል የምቃወምበት ምክንያት አይኖረኝም ነበር::ችግሩ ግን በዛን ጊዜ አንቺን እርጉዝ ነበረች::የአራት ወር አርጉዝ ነበረች….‹‹ልጄን ይዘሽ ይሄንን የመሰለ አደጋ ልጋፈጥ ስትይኝ ቁጭ ብዬ አላይሽም ››አልኳት
‹‹ታዲያ ምን ይሁን? ግደሉት ብዬ ብቻውን ልልቀቀው ወይ…?››ብላ ህሊና የሚሞግት ጥያቄ አቀረበችልኝ
‹‹እኔ እስከፈለግሺው ቦታ ይዤው እሄዳለው::ይሄን አደጋ ለመጋፈጥ ካንቺ ይልቅ እኔ እሻላለው››የሚል ሀሳብ አቀረብኩላት
በወቅቱ አሻፈረኝ አይሆንም አለች….‹‹ለምን…?››ያቀረብኩላት ጥያቄ ነበር
‹‹የሆነ ነገር ከሆንክ ምን ብዬ አወራለው ነው ያለቺኝ…‹‹በእኔ ቤተሰብ ይሄንን ያህል መከራ እንድትጋፈጥ አልፈቅድም›› አለቺኝ ….በዚህ ጉዳይ ከሁለት ቀን በላይ ተጨቃጨቅን… ቡኃላ ሽማግሌም መሀላችን ገብቶ በእኔ መሄድ ተስማማን…
ከዛ እኔና አጎትሽ ጨላማን ተገን አድርገን ከአዲስ አበባ በእግር ወጣን .. ግማሽ መንገድ በግር ሲመቻችልን ደግሞ መኪና በመጠቀም ሞያሌ ድረስ ሸኘውት..እዛ ለመድረስ 8 ቀን ነበር የፈጀብን…ከዛ ደላሎች ወደኬንያ እንዲያሸጋግሩት አመቻችቼ…ድንበር ማቋረጡንም ካረጋገጥኩ ቡኃላ በስኬት ተመለስኩ….
‹‹ከዛስ…?››
‹‹ከዛማ…ከከተማ ይዤው ወጥቼ እንዳስመለጥኩት ደህነቶች መረጃ ደርሶቸው ነበረና እቤቴ ሳልገባ ከመንገድ ነው የጠለፉኝ…››
‹‹ወይ አባ አንተን..…?ታዲያ ምን አደረጉህ…?››
‹‹ከዛም አሁን ሙዚዬም ይሁን ተብሎ የተዘጋው ማዕከላዊ አስገቡኝ::በፊልም ላይ አይቼው ማለውቀውን..በመፃፍም ላይ እንኳን ማንበቤን ትዝ የማይለኝን አይነት ስቃይ አሰቃዩኝ::መፈጠሬን እስክጠላ…ሰው ምን አይነት ፍጡር ነው? ብዬ እስክጠይቅ ድረስ……?እግዜር እንዴት እንደዚህ አይነት ፍጡር ይፈጥራል…? ብዬ ሙግት ውስጥ እስክገባ ድረስ….‹‹እግዜር ሰውን በመፍጠሩ ተፀፀተ› የሚትለው መፃፍ ቅዱስ ላይ ከአመታት በፊት ያነበብኩት ጥቅስ ትርጉም በደንብ እስኪገባኝ ድረስ አሰቃዩኝ››
‹‹አንተን..?ስለአስመለጥከው ብቻ…?››
‹‹አዎ …የት ነው ያደረስከው..…?በድርጅቱ ውስጥ አንተስ የነበረህ ኃላፊነት ምንድነው?ውጭ ካሉት ጋር መመሪያ እየተቀበልክ ክፍለሀገር ላሉት አባሎቻችሁ ሽብር እዲፈፅሙ ምታሰማራቸው አንተ ነህ ወይ?ቀጣዩ የድርጅቱ እቅድ ምንድነው?ሌሎችስ እዚህ ከተማ ውስጥ ሆነ በሌሎች የኦሮሚያ ከተሞች ያሉ አባሎቻችሁን ዝርዝር ?›› የማይጠይቁኝ ጥያቄ የለም..እያንዳንዶ ነጠላ ጥያቄ ከብዙ ማሰቃየትና ገሀነማዊ ቶርቸር ቡኃላ ነበር የምትከተለው፡፡እንዴት አንድ ሰው በገዛ ወንድሙ ላይ በዚህ መጠን ሊጨክን ይችላል?ምን ለማግኘት …?ስንት ዓመት በዚህ ምድር ላይ ለመኖር?በፓለቲካ ልዩነት ብቻ የገዛ ወገንን በየምክንያቱ ከዚህም ከዛም እየሰበሰብ በጭለማ ቤት አጉሮ ጥፍር እየነቀሉ እና ብልት ላይ ሀይላንድ እያንጠለጠሉ በማሰቃየት የሚያስገኘው ውጤት ስልጣን ብቻ አይደለም ዘላለማዊነትስ ቢሆን ያዋጣል እንዴ?በእኔ ሚዛን አያዋጣም፡፡ያንን መከራ በራሴ ላይ ደርሶ ከማያቴ በፊት በሰው ልጅ ላይ የሚሰራ የመጨረሻው አሰቃቂ ወንጀል ወይም ግፍ ግድያ ይመስለኝ ነበር…አንድን ሰው ግንባሩን በጥይት አፍርሶ መግደል፡፡ለካ አሱ ቸር እና አዛኝ የሆኑ ወንጀለኞች የሚፈጽሙት ቀላል ከሚባሉ ቅጣቶች ውስጥ የሚካተት ነው?ብዙም ሊጨክኑበት የማይፈልጉትን ሰው በእንክብካቤ የሚያስወግዱበት ዘዴ…ይህንነ አሁን እየተነጋርኩ ያለውትን ንግግር ሴሜቱ በትክክል የሚሰማው ተመሳሳዩ ነገር የደረሰበት ሰው ብቻ ነው፡ግን ከሰው ውጭ ሌላ ፍጡር በራሱ ፍጡር ላይ ይሄንን ያህል ይጨክናል?ለምሳሌ አንበሳ በአንበሳ
👍5
ላይ?ጅብ በጅብ ላይ…? ነብር በነብር ላይ..…?በፍጽም አይመስለኝም፡፡እና እኛ ከአውሬዎቹ በላይ አውሬነት በውስጣችን ተሸክመን የምንዞር አደገኛ ፍጥሮች ነን ማለት ነው…?፡፡
‹‹እንዴ አንተ ኦነግ ነበርክ እንዴ…?››
‹‹ወይ ኦነግ…የት ብዬ?አንደኛ እኔ በወቅቱ በነበረው የኦነግ የፖለቲካ ፕሮግራም የማምን ሰው አልነበርኩም፡፡ሁለተኛ የማምንበትም ቢሆን እንኳን እኔ በፓለቲካ ጫወታ የሚያስደስተኝ አይነት ሰው አይደለውም፡፡እና እንኳን ልሆን ቀርቶ ኦነግ የሆነ ሰው የማውቀው እጎትሽን ብቻ ነበር፡፡ግን ለእነሱ እሱን እንዲያመልጥ መርዳቴ እና ስሜም ገመዳ መሆኑ ብቻ ለኦነግነቴ በቂ እንደውም ከበቂ በላይ መረጃ ነበር…››
‹‹እሺ ታዲያ እንዴት አደረጉህ…?››የዚህ አሰቃቂ ታሪክ መጨረሻ ማወቅ ጓጓው…አናቴን እዚህ ስሬ ቁጭ ብሎ እያየውት ገድለውት ይሆን እንዴ…? ብዬ እስካስብ ድረስ፡፡ምን ማለቴ ነው…? ያለፈውን ታሪኩን እየነገረኝ ስሬ ቁጭ ብሎ እየነገረኝ ያለው በህይወት ስለተረፈ አይደል እንዴ…? ለአንድ ወር ያህል የአምላክ እርግማን እንደወረደበት እባብ ከቀጠቀጡኝና ከተለተሉኝ ቡኃላ ምንም የሚፈልጉትን መረጃ ሲያጡ ደከማቸው መሰለኝ ጨለማ ቢት ወረወሩኝ፡፡ከሚሸት ቁስሌ፤ከሚከረፋ ላቤ ጋር ድቅድቅ ጨለማና የታፈነ ቤት ወስጥ ወረወሩኝ፡፡ለአንድ ሰው የመጨረሻው ቅጣት ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ…? ብቻውን እንዲሆን ማድረግ፡፡ በብቸኝነት ላይ ጭለማ፤ ረሀብና ጥማት ስትጨምርበት በቃ ሁሉን ነገር ነው የምትጠይው… እያንዳንዷን ደቂቃ እንዴት እንደምትረዝምብሽ ልነግርሽ አልችልም?ሰው በተፈጥሮ ብቻውን እንዲኖር አይደለም የተፈጠረው….መከራም ሆነ ስቃይ ረሀብም ሆነ መታረዝ ከሰው ጋር ከሆነ ይችለዋል…፡፡ማንኛውም እስረኛ ጨለማ ቤት ውስጥ ለብቻው ስድስት ወር ከሚዘጋበት ከሰው ጋራ እድሜ ልክ ቢታሰር ይምርጣል….፡፡
እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩም…
‹‹ቡኃላ እናትሽ በምታውቃቸው ሰዎችን የእያንዳንዱን ባለስልጣን ደጅ ፀንታ ለአራት ለአምስቱ ባለስልጣናት ያላትን ብር አስረክባ አስፈታቺኝ…፡፡ቀጥታ ከማዕከላዊ በለሊት አምጥተው በራፎ ላይ ጣሉላት፡፡ወዲያው አፋፈሳ ሆስፒታል ወሰደቺኝ …አንድ ወር ከ15 ቀን አልጋ ይዤ ተኛው…በስንት ጥረት እና የህክምና እርዳታ በመጨረሻ ዳንኩ፡፡ግን አንድ የዘላለም ጠባሳ ሸልመውኝ ነበር…ፈጽሞ ልድነው የማልችለው››
‹‹ምን..?››
‹‹የዘር ፍሬዬን አፍርሰውት ነበር፡፡ሽንት ለመሽናት ከምጠቀምበት በስተቀር ለሴት የሚሆን የስሜት መነሳሳት ሆነ የማድረግ ችሎታ እንዳይኖረኝ አድርገውኝ ነበር…እና ይህ እንደተፈጠረ እናትሽን በዛ ወጣትነት ጊዜዋ ቀሪ ዘመኗን ሙሉ ከእኔ ጋር እንድታባክነው አልፈለኩም ነበርና እንድንፋታ የተቻለኝን ጥሬ ነበር፡፡ግን ይሄው 25 ዓመት እስከዘሬ አልተሳካልኝም፡፡በዚህ ታሪክ ውስጥ በእሷ ልክ የተጎዳ የለም፡፡የእኔ እንኳን አንዴ የሆነው ሆኖብኛል.. እሷ ግን ሁሉን ነገር ማድረግ እየቻለች ነው…፡፡እናም ደግሞ አብራኝ እንዳትተኛ እና እልጋችንም እንዲለያየ ያስገደድኳት እኔ ነኝ ፡፡ሰውነታችን ሲነካካ የእሷ አካል ሲግል እኔ ግን በንዴትና በቁጭት ሲሸማቀቅ፤ እሷ ልትሰመኝ ሲያምራት እኔ ደግሞ ያንን እያየው ስሳቀቅ ..፡፡በቃኝ አልኳት..፡፡በቃን አካላችንን በማነካካት ስቃያችንን ለምን ገሀነማዊ እናደርገዋለን እልኳት…?ጥዬሽ እንዳልጠፋ ከፈለግሽ በማሀከላችን ያለውን ክፍተት ጠብቂ አልኳት.፡፡.መለያየት የለብንም ምትይ ከሆነ የፈለግሽውን ነገር በፈለግሽ ጊዜ ከሌላ ሰው ጋር በውጭ ብታደርጊ ምንም ተቃውሞ የለኝም አልኳት …፡፡ሀሳብሽን ቀይረሽ መፋታት አለብኝ በምትይበት ቀን በደስታ እሸኝሻለው ብያታለው፡፡ያው እስከዛሬ ያንን ጥያቄ ይዛ አልመጣችም..እና አልጋችንንም ብቻ ሳይሆን መኝታ ቤታችንንም እንደለየን ይሄው ለዓመታት አለን፡፡
ተቃቅፈን እስኪደክመን ድረስ ነው የተላቀስነው……አንዳችን አንዳችንን ማፅናናት አላሰኘንም፤ አልሞከርንምም፡፡አዎ የምንወደውን የጋራ ዘመዳችንን እንደተረዳን ነገር ነው ሁኔታችን፡፡እያንዳንዱ ሰው ለካ በውስጥ የሆነ ሀገር የሚያህል ሚስጥር ቀብሮ ነው የሚኖረው፡፡እንዴት ይሄን ጉድ እኔ ልጃቸው እንኳን ሳላውቅ እንባውን እየጠራረገ እና የኔንም እያበሰልኝ መናገሩን ቀጠለ‹‹እና እናትሽ ለእኔ ስትል ነው እንዲህ የሆንከው የሚል ፀፀት ውስጧን እንዳሰቃያት ነው..ለዛ እራሷን በመቅጣት እድሜዋን ጨርሳዋለች፡፡እንደዛ የተበሳጨችብሽ ለዛ ነው፡፡ቁስሏን ነካክተሸ ስለደማሽባት…››
‹‹አሀ እኔንም ከተወለድኩ ጀምሮ ትኩረት ምትነፍገኝ በዚህ ታሪክ ምክንያት ነዋ..እኔን እርጉዝ ሆና ባይሆን እሷ ነበረች የምትሄደው..አንተ ላይ ሚደደረስብህ ነገር አልነበረም..እና እኔን ስታይ በአንተ ላይ የደረሰው መከራ ነው የሚታያት ማለት ነው..አይደል..?፡፡››
‹‹እሱን እርሺው ልጄ ..አንዳንድ ነገሮች እኛ ፈለግንም አልፈለግንም መሆን ባለበቸው መልኩ ከመሆን አያመልጡም፡፡ያው መቼስ እኛ ሰዎች ነንና እንዲህ ቢሆን ኖሮ …?እንዲ ባደርግ ኖሮ እያልን በፀፀት እራሳችንን እንቀጣለን እንጂ መሆን ያለበት ይሆናል››
‹‹አንድ የመጨረሻ ጥያቄ››
‹‹አሁንማ ዋናውን ነገር አውቀሻል.. የፈለግሺውን ጠይቂኝ… ከነገርኩሽ በላይ ሚከብድ ጥያቄ ልትጠይቂኝ አትቺይም..››
‹‹እማዬ…?›› ጥያቄውን ጀምሬው መጨረሱ ከበደኝ
‹‹እማዬ ምን..?››
‹‹እማዬ ታዲያ ይሄን ሁሉ አመት ..ማለቴ ጓደኛ እንኳን የላትም ብለህ ታስባለህ?ማለት ላንተ ላትነግርህ ትችላለች…››
‹‹ግዴለም ሳትጨናነቂ ጠይቂኝ ….ለማለት የፈለግሺው ገብቶኛል…በስንት ውትታና ጭቅጭቅ ከአስር አመት በፊት አንድ በጣም የሚወዳት ሰው ነበርና ከእሱ ጋር ጀምራ ነበር….እኔ አውቄ ማለት ነው ..ነግራኝና አስፈቅዳኝ፡፡አስፈቅዳኝ ብቻ ሳይሆን ገፋፍቼያት፡፡እንደዛ ብታደርጊ እኔም ስለአንቺ መጨነቁ ይቀንስልኛል ብያት..››
‹‹ታዲያ እንዴት ሆኑ..?››
‹‹ስድስት ወር እንኳን አልዘለቀችበትም..››
‹‹ምነው ..?ተጣሉ.. ..?››
‹‹አይ መጣላት እንኳን አይመስለኝም….ሰውዬው በፊት ከሚያፈቅራት በላይ እያፈቀራት ሲመጣ ይረብሻት ጀመር…››
‹‹እንዴት እድርጎ ነው የሚረበሻት..?››
‹‹ትተሸው ነይ ላግባሽ እያለ ነዋ››
‹‹እንዴ!!!! ሰውዬው በአንተ ላይ ስለተፈጠረው ነገር ያውቃል እንዴ..?››
‹‹በፍጽም አያውቅም…፡፡ያው እንደማንኛውም ለትዳሯ ታማኝ እንዳልሆነች ሴት ወይም ባጋጣሚ እንደተሳሳተች እና ከእሱ ፍቅር ይዟት በዛው ግንኙነቱ ውስጥ የቆች አድርጎ ነበር የሚያስበው፡፡ግን ያ አይበቃኝም አለ…እሱም ሚስቱ የሞተችበት እና ለአመታት ብቻውን የሚኖር ነበርና ሙሉ በሙሉ ፈለጋት…››
‹‹ምን አይነት ደፋር ነው!!!››
‹‹ድፍረት አይደለም… እናትሽ አሻፈረኝ አለች እንጂ አኔም በሰውዬው ሀሳብ ተስማምቼ ነበር፡፡ለእናትሽ በጣም ጥሩ ሰው ነበር…ያፈቅራት ነበር…..በዛ ላይ ስራቸው አንድ ላይ ነው…››
‹‹ምን…..?ማነው አውቀዋለው…..?››
‹‹የአለቃሽ የፍሰሀ አባት ነው፡፡ሁለቱም የተለያዩ ካምፓኒዎችን ነበር የሚመሩት ከዛ አዋህደውት ነው አሁን የምታውቂውን ግዙፍ ካምፓኒ የመሰረቱት፡፡ግን በትዳሯ መወሀድ ካምፓኒዎቻቸውን እንደማዋሀድ ቀላል አልሆነላቸውም....››
‹‹አሁን ገባኝ…››
‹‹ምኑ ነው የገባሽ..?››
‹‹አይ ከምሰማቸው ነገሮች ተነስቼ ብዙ ጊዜ በዚህ ሰውዬ እና በእናቴ መካከል የሆነ አለመጋባባት እንደለ እገምት ነበር….አሁን ምክንያቱ ግልጽ ሆነልኝ…ሁለቱም የየራሳቸው ልጆች ካምፓኒውን ተረክበው እንዲመሩላቸው አጥብቀው የሚጥሩበትንም ዋና ምክንያት ተገለፀልኝ…..ሳያስቡት
ጦርነት ውስጥ ገብተዋል….››
‹‹ይሆናል ››አለኝ አባቴ….
‹‹አዎ እንዳዛ ነው ..››አልኩት
‹‹አንድ የመጨረሻ ነገር ልንገርሽ››
‹‹ምንድነው አባ››
‹‹አጎትሽ..ያ አስመለጥኩት ያልኩሽ፡፡ከዘመናት የስደት ኑሮ ቡኃላ ሰሞኑን ሊመጣ ነው፡፡ በመንግስት ጥሪ ወደሀገሩ ሊመለስ መሆኑን ደውሎ ነግሮኛል…››
‹‹የራሱ ጉዳይ›› አልኩት
‹‹ዝም አለኝ…
ሁለታችንም ድክምክም ብለን በስካር እና በሀዘን አንገታችንን ደፍተን… ተደጋግፈን ወደመኝታ ቤታቸን ስንሄድ ከላሊቱ 10 ሰዓት አልፎ ነበር ፡፡እንደገባን አልጋችን ላይ ወጥተን እቅፍቅፍ ብለን ስንተኛ ወደጆሮ ተጠጋውና ‹‹አባ አይዞህ እሺ እኔ ልጅህ ሁሌ ከእቅፍህ ውስጥ አልወጣም …ሁሌ …እና ደግሞ በጣም ነው ውደድድድድ ማደርግህ››አልኩት
ግንባሬን ሰመና ‹‹አውቃለው …እኔም ሁለ ነገሬ ነሽ….አሁን ሁሉን ነገር እርሺና ተኚ ››አለኝ
‹‹እ……ሺሺሺሺ››ረጂም ትንፋሽ...


💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
አትሮኖስ pinned «#ፍቅር_ከፈላስፋ ፡ ፡ #ክፍል_ሀያ_አምስት ፡ ፡ ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ ፡ ፡ ❤️ፌናን === ‹‹….ምን አልባት ትክክል ነሽ››አለኝ ‹‹ምኑን አባ…?›› ‹‹እውነቱን የማወቅ መብት አለሽ …እናም ነገርሻለው›› አቀማመጤን አስተካከልኩ..በስካርና በድካም እየታጠፉ የነበሩ ጆሮዎቼን ሲነቃቁና ሲዘረጋጉ ይታወቀኛል… ‹‹በዚህ የታፈነ በምትይው የእኔ እና የእናትሽ ኑሮ ውስጥ ባጣም ተጎጂው እኔ ሳልሆን…»
#ፍቅር_ከፈላስፋ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት



ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ



#ፍሰሀ
===
በህይወቴ በጣም የተፈተንኩበት አንድ ሳምንት ነው እያሳለፍኩ ያለውት…በጣም አስጨናቂና ትንፋሽ የሚያሳጣ አይነት ሳምንት…. ደግነቱ ስራዎቼን ቀድሜ ማጠናቀቄ በጀኝ እንጂ በዚህ አይነት የጨፈገገ ስሜት እንዴት እሰራው እንደነበር ማሰቡ እራሱ ይከብደኛል ፡፡
ምክንያቱ አለመኖሯ ነው……ይሄው አይኖቼ አይኖቾን ካዩ አንድ ድፍን ሳምንት ተቆጠረ…የቤተሰብ ጉዳይ ስላጋጠመኝ ድሬደዋ ሄጃለው ነበር ያለቺኝ…እኔማ ደርሶ መልስም ቢሆን ልምጠና አንዴ አይቼሽ ልመለስ ብያት ነበር..ብትመጣም አታጋኘኝምና አትልፋ.. ይልቅ ዝግጅትህ ላይ አተኩር ፤ፍልሚያውን በድል ከተወጣህ ቡኃላ ደውልልኝ..እስከዛ እኔም እዚህ ያለውን ነገር ጨርስና እመለሳለው ካልሆነም ያለውበትን አድራሻ እነግርህና ትመጣለህ›› ስላለቺኝ… ምርጫ አጥቼ በናፍቆቷ እየተሰቃየሁ ባለቺው ተስማምቼ እጄን አጣጥፌ ቁጭ አላልኩም፡፡ምናልባት ድሬደዋ የሄደችበትን አድራሻዋን ባገኝ ብዬ ከሶስት ቀን በፊት በፊት ትሰራበት ወደነበረ ከዚህ በፊትም እንዲህ በጠፋችበት ጊዜ ወደአገኘዋት ሜክሲኮ መጽሀፍት ቤት ሄጄ ነበር ……መኪናዬን ቦታ አስይዤ በማቆም ወደ መጻሀፍ መደብሩ አመራው::ሁለት በአስራዎቹ መጨረሻ ዕድሜ ላይ የሚገኙ ወጣቶች ናቸው ያሉት…አንደኛው ደንበኛ እያስተናገደ ስለነበረ ነፃ ወደሆነው ተጠጋሁ…
‹‹ምን መፃሀፍ ልስጥህ…..? ››አለኝ… እዚህ ቤት መፃሀፍ እንጂ ሴት ፍለጋ የሚመጣ ሰው ይኖራል ብሎ ስላልገመተ መሰለኝ ቀጥታ ስለመፃፍ የጠየቀኝ ፡፡
‹‹ፌናንን ፈልጌ ነበር..ሰሞኑን መጥታ ነበር?››
‹‹አይ ቆየች.. አስራ አምስት ቀን ሆኗታል››
‹‹ጓደኛዋ ነኝ …ማለቴ የመስሪያ ቤት ጎደኛዋ..ስልኳ አልሰራ ብሎኝ ነው ..ቢሮ ደግሞ እሷ ብቻ የምትሰራው አፋጣኝ ስራ ነበር..እና እቤቷን ልትጠቁመኝ ትችላለህ፡፡››
‹‹እቤታቸው ቤቴል አካባቢ እንደሆነ ነው እንጂ ትክክለኛውን ቦታ አላውቅም…ግን ትንሽ ብትጠብቅ እኮ ጋሼ ስለሚመጡ ትጠይቃቸዋለህ››
‹‹ጋሼ ማነው…..?››
‹‹አባቷ ናቸዋ››
‹‹እርግጠኛ ነህ ይመጣሉ?››
‹‹አዎ እንደሚመጡ ደውለው ነግረውኛል፡፡››
‹‹አይ እንደዛ ከሆነማ አሪፍ ነው.. እጠብቃቸዋለው ››አልኩ…ግን ደግሞ ወዲያው ሌላ ጥያቄ በውስጤ ተፈጠረ…‹‹ከአባቷ በጣም ትግባባላችሁ ማለት ነው?››ጠየቅኩት
‹‹እንዴ አሰሪዬ አይደሉ ለምን አንግባባም?››ሲለኝ እየገባኝ የመሰለኝ ጉዳይ መልሶ ድንግርግር አለብኝ
‹‹አሰሪዬ ስትል..…..?››
‹‹ይሄ የመፅሀፍ መደብር እኮ የእሷቸው ነው …ሌላም ቦታዎችም አላቸው››ሊያብራራልኝ ሞከረ…
‹‹ይሄ መጻሀፍ ቤት የፌናን አባት ነው?››
‹‹አዎ ››አለኝ ይሄን ሁሉ ሳታውቅ ነው እንዴ ጓደኛዋ ነኝ የምትለው በሚል ስሜት ..
ገረመኝ..ከዚህ በፊት እዚህ ባገኘዋት ጊዜ በትርፍ ጊዜዋ ተቀጥራ እንደምትሰራ ነበር የነገረቺኝ ፡፡ይሄ ሁሉ መዋሸት ለምን አስፈለገ?
በውስጤ የተፈጠረ የመደነቅ ጥያቄ ነበር…
‹‹አባቷ ጎበዝ ናቸው ማለት ነው?››አልኩት ልጁን….ስለእዚህች ሚስጥር ስለሆነች ልጅ ሌላ ተጨማሪ ሚስጥር እንዲነግረኝ በመፈለግ ለመጎትጎት ፈልጌ
‹‹እንዴ…!!!››አለና ዝም አለ
‹‹ምነው…..?››
‹‹ጋሼን አታውቃቸውም እንዴ?››
ነገሮች እንዳይበላሹ ዋሸውት‹‹አውቃቸዋለው››
‹‹አይ ጎበዝ ናቸው ስትል ገርሞኝ ነው››
‹‹ለምን ይገርምሀል…..?››
‹‹ጎበዝ ናቸው ማለት ነው ስትል በጉብዝናቸው ጥርጣሬ ያለብህ ይመስላል..እሷቸው እኮ ይሄንን የከፈቱት እኛንም ለመርዳት ነው እንጂ ጎበዝ ለመሆን አይደለም…አስተማሪነታቸው እና ደራሲነታቸው ብቻ ለጉብዝናቸው በቂ ነው››
‹‹እሱስ እወነትህን ነው››አልኩት ልክ አስተማሪም ሆነ ደራሲ መሆናቸውን እንደማውቅ ሆኜ…‹‹ አሀ የአስተማሪና የደራሲ ልጅ ነሻ?.ለዛ ነው ነገሮችን መበታተን እና መልሶ መሰብሰብ ሚያስደስታት….አሁን ገባኝ››ብዬ በወስጤ አብሰለሰልኩ…አሁን በዘዴ ብዙ ነገር እያወቅኩ ነው…ይበልጥ ለማወቅ ሌላ ዘዴ መጣልኝ፡፡
‹‹እስቲ የእሳቸው መፃሀፍ ይኖራል..…..?››
‹‹የቱን ልስጥህ……..?››
‹‹ሁሉንም የለኝም… አሪፍ ያልከውን …››
በፈገግታ ከዚህም ከዛም አየመዘዘ አምስት መፃሀፍ እጄ ላይ ዘረገፈ…
‹‹እንዴ…? ይሄን ሁሉ እንደፃፍ አላውቅም ነበር››መደነቄን መደበቅ አልቻልኩም
‹‹11 መፃሀፍ እኮ ነው ያላቸው..ይበዛብሀል ብዬ ነው የቅርቦቹን ብቻ መርጬ የሰጠውህ…. ልጁን እያዳመጥኩ ግን ደግሞ መፃሀፎቹን እያገላበጥኩ በማየት ላይ ሳለው አይኖቼ የመፃፍ ጀርባ ላይ የታተመ የደራሲው ፎቶ ላይ አረፈ ..ደነገጥኩ…. እባብ ሱሬው ውስጥ እንደገባበት ሰው አይነት ነው አደነጋገጤ ..ሰውዬውን አውቃቸዋለው፡፡ሌላውን መፃሀፍ ጀርባ ገለበጥኩ ፎቶ የለውም……ሌላውን ገለጥኩ አዎ እራሳቸው ናቸው…ከመቀመጫዬ ተነሳው….
‹‹ሂሳቡ ስንት ነው…..?››
‹‹የየትኛው…..? ››
‹‹የሁሉም››
መፃሀፎቹን ከእጆቼ ወሰደና ጀርባቸው ላይ ያለውን ዋጋ ደምሮ ነገረኝ..ከፍዬ መልስም ሳልጠይቅ ወጣሁ…
‹‹እንዴ አትጠብቃቸውም……..?››ልጁ ግራ ተጋብቶ ጠየቀኝ
‹‹ተመልሼ መጣለው ››ቻው..ተንደርድሬ መኪናዬ ውስጥ ገባውና አሁንም ድጋሜ የመጽሀፉን ጀርባ ላይ ያለውን ፎቶ አየሁት…ንዴትም ደስታም የተቀላቀለበት ስሜት ነው ተሰማኝ፡፡እኚን እኮ ነው ሹገር ዳዲዋ እንደሆኑ የነገረቺኝ ፡፡ለካ አባቷ ናቸው…?ሲያስደስት..ግን እንዴት ነው የምታስበኝ ?ይሄን ሁሉ ውሸት እንዴት ስትዋሸኝ ትከርማለች……? ስለእሷ የማላውቀው ሌላስ ምን አለ……?ይህቺ ልጅ እስከመቼ ነው እየራቀቀችብኝና እየጠለቀችብኝ የምትሄደው…?ለማንኛውም በእሷ በመታለሌ ከተበሳጨውት ይበልጥ ሹገር ዳዲዋ ናቸው ብዬ ለቀናት በንዴት ስንጨረጨር እና እንቅልፍ ሳጣበት የነበረው ጉዳይ ውሸት ሆኖ አባቷ በመሆናቸው የተደሰትኩት በእጥፍ ይበልጣል…
ከዛን ቡኃላም ስልኳ አይሰራም…ካላጋነንኩት ለመቶ የቀረብ መልዕክቶችን ልኬላታለሁ…ምንአልባት ከከፈተችው ወዲያው እድትደውልልኝ በማለት..ግን አንደዛ አልሆነም…ይገርማችሆል አንዳንዴ በውድቅት ለሊት ስምንትና ዘጠኝ ሰዓት ከእንቅልፌ ድንገት በርግጌ እነሳና ስልኬን አንስቼ እሞክርላታለው….ግን የተለወጠ ነገር አልነበረም፡፡ዛሬ ግን በተቻለኝ መጠን ስለእሷ ከማሰብ እራሴን መግታትና እና ትኩረቴን ሰብሰብ አድርጌ ስለፍፃሜው ጦርነት ብቻ ማሰብ ነው የምፈልገው፡፡ቀኗ ዛሬ ነች…ማንነቴን ለአባቴም ለሌላውም ሰው የማሳይበት ቀን፡፡ይህቺን ቀን አብራኝ ለወራት የለፋችው ፊናን ከጎኔ ብትሆን ኖሮ የበለጠ ጠንካራ የበለጠ ልበሙሉ እሆን ነበር…አይ የኔ ነገር አሁንም መልሼ ወደእሷ ወሰድኮችሁ አይደል፡፡

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍51
አትሮኖስ pinned «#ፍቅር_ከፈላስፋ ፡ ፡ #ክፍል_ሀያ_ስድስት ፡ ፡ ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ ፡ ፡ #ፍሰሀ === በህይወቴ በጣም የተፈተንኩበት አንድ ሳምንት ነው እያሳለፍኩ ያለውት…በጣም አስጨናቂና ትንፋሽ የሚያሳጣ አይነት ሳምንት…. ደግነቱ ስራዎቼን ቀድሜ ማጠናቀቄ በጀኝ እንጂ በዚህ አይነት የጨፈገገ ስሜት እንዴት እሰራው እንደነበር ማሰቡ እራሱ ይከብደኛል ፡፡ ምክንያቱ አለመኖሯ ነው……ይሄው አይኖቼ አይኖቾን…»
#ፍቅር_ከፈላስፋ


#ክፍል_ሀያ_ሰባት



ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ


#ፍሰሀ


ብቻ አሁን ከንጋቱ 12 ሰዓት ነው…መኝታዬን ለቅቄ ቢጃማዬን እያወላለቅኩ ወደሻወር ቤት አመራው…የሻወሩን ውሀ ለብ እንዲል አደረግኩና ገባውበት…አዎ ንጹህና ቀለል ብሎኝ መዋል ነው የምፈልገው፡፡
ዛሬ የምለብሰውን ልብስ ከአስር ቀን በፊት ነበር የተዘጋጀው…ሙሉበሙሉ በፌናን ምርጫ በጥንቃቄ ተመርጠው የተገዙ አዳዲስ ናቸው፡፡ከሻወር ወጥቼ እራሴን ካደራረቅኩ ቡኃላ ከቁም ሳጥኔ ውስጥ እያወጣው ሙሉ ቁመናዬን በጥራት የሚያሳየ መስታወት ፊት ቆሜ በጥንቃቄ ለበስኩ፡፡ፀጉሬን አስፈላጊውን ቅባት በተገቢው መጠን በመቀባት አስተካከልኩ፡፡ካሉኝ ሽቶዎች ምርጥ የተባለውን ሽቶ ሳይበዛም ሳያንስም ከተጠቀምኩ ቡኃላ ለመጨረሻ ጊዜ መስታወቱ ፊት አየተሸከረከርኩ..እየቀረብኩ ..እየራቅኩ የጎደለ ወይም የተዛነፈ ነገር ካለ አረጋገጥኩና ስልኬንና የመኪና ቁልፌን ይዤ ከመኝታ ቤቴ ወጣው
በዚህን ጊዜ ለአንድ አስር ጉዳይ ሆኖ ነበር፡፡ፕሮግራሙ የሚጀመረው ሶስት ሰዓት ስለሆነ ገና ቡዙ ጊዜ አለኝ፡፡አባቴ እየተዘጋጀ መሆኑን ለማረጋገጥ ወደእሱ መኝታ ቤት አመራው…፡፡አዎ ተንስቷል… ምክንያቱም መኝታ ቤቱ ገርበብ እንዳለ ነው፡፡እየተቃረብኩ ስመጣ ድምጹን ሰማው …ያወራል፡፡ስልክ ላይ እንደሆነ ገባኝና ልመለስ ስል ከአንደበቱ ወጥተው ጆሮዬ የደረሱ ዓ/ነገር ጭራሽ ተጠግቼ እንዳዳምጥ ገፋፋኝ፡፡የኮቴዬን ድምጽ እንዳይሰማ ተጠንቅቄ ወደ በራፉ ቀረብኩና አጨንቁሬ ወደውስጥ እያየው ጆሮዬን ለጠፍኩ፡፡አባቴ ፊቱን ከበሩ በተቃራኒው አዙሮ የአልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጦ እያወራ ነው፡፡
‹‹ስሚኝ ክብረወርቅ …ዛሬም ድረስ እንደማፈቅርሽ አትዘንጊ››ይሄንን መስማቴ ነው በፈገግታ ቀሪውን የስልክ ልውውጥ እንዳዳምጥ የገፋፋኝ..‹‹አባዬ ውሽማ አለችው እንዴ..?..የሚገርም ነው….››
ከዛኛው ወገን የሚነገረው ከርቀቱ አንጻር አይሰማኝም…
‹‹ይሄውልሽ…አንቺ ለልጅሽ እንደምታዳይ ሁሉ እኔም ልጄ የፈለገውን እንዲያገኝ የማልፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም››
‹‹አይደለም..ፈፅሞ አንቺን ለመበቀል እየሰራው ያለውት ስራ የለም፡፡እርግጥ ለዓመታት እንድታገቢኝ ስማፀንሽ አሻፈረኝ ስላልሺኝ ሁሌ እንደተበሳጨውብሽ ነው፡፡አሁንም ከንዴቴ ጋር ነው ያለሁት…፡፡ቢሆንም ግን ላንቺ ያለኝ ፍቅር እዛው ድሮ ያለበት ቦታ እንደሆነ ልደብቅሽ የሚያስችል ጥንካሬ አይኖረኝም…
‹‹አዎ ባል እንዳለሽ አንድ ሺ ጊዜ ነግረሺኛል..አውቃለውም…፡፡ግን አንቺ ለእኔ የተፈጠርሽ ሴት ነበርሽ፡፡ባልሽ እኮ ምኑም ካንቺ ጋር አይሄድም፡፡አንቺን የምታህል ሚኒዬነር ነጋዴ አንድ ተራ የሀይ-እስኩል አስተማሪ አግብታ እድሜ ልኳን ከእሱ ጋር……….››
‹‹ይቅርታ ..ሁል ጊዜ ስለእሱ ሳወራ እንደምትበሳጪ አውቃለው፡፡ግን እይውእስቲ…እኔ እና አንቺ በጋራ ይሄን የመሰለ ካምፓኒ መመስረት ችለናል፡፡ለአመታት በጣም ውጤታማ ነን፡፡ይሄንን የቢዝነስ ስኬታችንን ለልጆቻችን አስተላልፈን እኔና አንቺ ወደ ፍቅር ውህደት ማለቴ ወደ ትዳር ብንገባና ቀሪ ዘመናችንን የተረጋጋ እና የሰከነ ኑሮ ብንኖር ደስ ይለኛል፡፡ምንኖረው ሀገር ውስጥም ላይሆን ይችላል ፡፡አንቺ ተስማሚ እንጂ የፈለግሽው የሀገር ጫፍ ብትይ ይመቸኛል፡፡ሰው ማይኖርበት አንታርቲካም ቢሆን ..››
‹‹የምሰማው ንግግር ከአባቴ አንደበት እየወጣ መሆኑን ማመን ተሳነኝ ‹‹…ወይ ጉድ!! ለካ ሼባው አደገኛ የፍቅር አክተር ነበረና…እኔ እንኳን እሱ በሚያወራው መጠን የማወራትና የምጀነጅናት ሴት ኖራኝ አታውቅም….. ደግሞ ተፈቃሪዋ እኮ የካምፓኒው አንዷ ባለድርሻ ነች …ለካ ይህ ጉዳይ ለእሱ ወሳኝ እንደሆነ ለመቶ ምናምነኛ ጊዜ ደጋግሞ ሲነግረኝና ሲያስጠነቅቀኝ የነበረው ሌላ ምክንያት ስላለው ነበር… አዎ አሁን ገባኝ … በመካከላቸው ያለው ጦርነት ቢዝነሳዊ ብቻ ሳይሆን ፃታዊም ነበር ማለት ነው…፡፡
‹‹ቀጥሏል አባቴ››
‹‹…በቃ እንግዲህ ….የልጅሽና የልጄ ፊልሚያ ላይ እንገናኝ፡፡እና የመጨረሻው ደስታ የእኔ ስለሚሆን ፅዋችንን በእኔ ወጪ ነው የምናነሳው…››
‹‹አታስቢ.. የልጄን ዕወቀትና ብቃት ስለማታውቂ ነው…እኔን ስለምታውቂኝ እሱንም ያወቅሽ እንዳይመስልሽ፡፡እኔን ቁጭ አድርጎ ሊያስተምረኝ ሚችል ጀግና ነው››
ከአባቴ አንደበት በዚህ አይነት ሁኔታ የራስን ልጅ ግነታዊ በሆነ ደረጃ ከፍ ከፍ እያደረገ ሲናገር መስማቱን አልወደድኩትም …ከዚህ የባሰ ነገር ተናግሮ ለወራት የገነባውትን ማንነቴን እና በራስ መተማመን እንዲሸረሽርብኝ ስለማልፈልግ ቀስ እያልኩ ወደኃላ አፈገፈግኩና ወደሳሎን ወረድኩ….
ሰራተኛዋ በምግብ ጠረጵዛው ላይ ቁርስ ደርድራ እንደጨረሰች አባቴም መጣ…
‹‹ፐፐፐፐ…ጠቅላይ ሚኒስቴር መስለሀል.››ብሎ ወደኔ ቀረበና ግንባሬን ሳመኝ..ደስ አለኝ…
ሌላውም ሰው እንደእሱ ከተሰማው አሪፍ ነው ስል አሰብኩ…በፌናን ምክር መሰረት አንዱ ነገር ተሳክቷል ማለት ነው…በዝግጅቱ ቀን የገምጋሚዎቹን ቀልብ ሰብስቦ የሚይዝ ፤በራስ መተማመንኔን በራሱ የሚያስረዳ አይነት አለባበስ መልበስ የመጀመሪያ መመሪያዋ ነበር…ሌላው ፕሮፖዛሉ ሙሉ ሰነድ እንደመሆኑ መጠን ከዛ ዋና ዋናውን ሀሳብ በአንድ ሰዓት ውስጥ ለሶስቱ ወሳኝ ሰዎች ለማቅረብ መከተል የሚገባኝን አካሄድ …
*
To make sticky idea you should be focuse on the following criteria
1/simplicity
2/un expected
3/Cridibel
4/concerete
5/Emotional
6/Story ……ትለኛለች
**
ሶስት ቀን ሙሉ ነው ስለእያንዳንዱ ነጥብ ምሳሌ በመስጠት ያስጠናቺኝ…፡፡እናም ጥናቱን ፍሬ ነገር ጨምቄ ቀላልና ግልጽ በሆነ አገላለጽ በገምጋሚዎች ላይ ያልጠበቁትን መደመም በመፍጠር ሚዛን ሚደፍ ሀሳቦችንና በሚያስምን አቀራረብ ሙሉ የጥናቱን ታሪክ በሚያስረዳ መልኩ የተጨመቀውን ሀሳብ በተሰጠኝ አንድ ሰዓት ውስጥ ማቅረብ እንድችል የተቻላትን ያህል አዘጋጅታኛለች… እኔም ብዙ ጊዜ እያፈረስኩ እየገነባው ሳምንቱን ሙሉ ተለማምጄዋለው፡፡እና አሁን ከአንድ ሰዓት ቡኃላ ይሄን የወራት ልፋቴን ውጤት የእኔም ብቻ ሳይሆን በዚህ መጠን እንድዘጋጅና ተፎካካሪዬን በብቃት እንድረታ በሚስችለኝ መጠን እንድዘጋጅ ለረዳችኝ ፊናን ልፋትም ፍሬው የሚለቀምበት ሰዓት ደርሷል፡፡ዝግጅቱን የማቀርብበት ሰዓት ….
በነገራችን ላይ ፕሮግራሙን ሳልነግራችሁ፡፡ከሶስት እስከአራት ሰዓት ባለው ጊዜ እኔ ሙሉ ሰነዱን አስረክቤ የተዘጋጀውበትን ሀሳብ በተሠጠኝ አንድ ሰዓት ውስጥ አቀርባለው…፡፡ከዛ ከአራት ሰዓት እስከ ተኩል ድረስ የምጠየቀውን ጥያቄ የምመልስበት ሰዓት ይሆናል፡፡. ከዛ የሻይ እርፍት ይኖርና፡፡ ከ5 እስከ ስድስት ሰዓት ደግሞ የሴትዬዋ ልጅ ትገባና በተመሳሳይ እንደ እኔ ያዘጋጀችውን ሰንድ አስረክባ በአንድ ሰዓት ውስጥ አቅርባ ስድስት ሰዓት ትጨርሳለች፡፡ከስድስት እስከ ስድስት ተኩል ልክ እንደእኔ በተመሳሳይ የጠየቋትን ጥያቄ የምትመልስበት ወቅት ይሆናል…፡፡
ከዛ አምስታችንም ወደምሳ ፕሮግራም እንሄዳለን፡፡ከ 6:30 እስከ 8 ሰዓት የምሳ ሰዓታችን ነው፡፡ከ8 እስከ 10 ሰዓት ሶስቱ የካምፓኒው ባለቤቶች ለብቻቸው ሰብሰባ ያደርጋሉ፡፡ በሰነዱና በቀረበላቸው ሀሳብ ላይ ይወያያሉ፡፡ለተኩል ሰዓት ሻይ ይወጣና ተፎካካሪዎቹም ባሉበት የመጨረሻ ድምጽ ይሰጣል፡፡የተሰጠው ድምጽ በግልጽ ሁሉም እያየ ይከፈታል አሸናፊው ይለይና ሙሉ ፕሮግራሙ ይጠናቀቃል፡፡
አሁን ከጥዋቱ 2፡40 ሆኗል እኔና አባቴ ቢሮ ደርሰናል፡፡ጋሼ ከበደ ከእኛ አምስት ደቂቃ ዘግይተው
👍4
ደረሱ… ሳላስበው ስሜታዊ ሆኜ ከወትሮ ሞቀ ባለ እና ቀብድ በሚመስል አይነት ሰላምታ ሰጠዋቸው፡፡እውነቱን ለመናገር አሁን ለማየት የፈለኩት ሴትየዋን ነው፡፡ወ/ሮ ክብረወርቅን ፡፡እወነቱን ንገረን ካላችሁ ምን እሷን ለማየት ጓጓለው ..ከዚህ በፊት ብዙ ጊዜ በአካልም በቴሌቬዝን ላይም አይቻታለው፡፡ስለዚህ ጉጉቴ ሌላ ነው …ለማየት የጓጓውት ልጇን ነው፡፡ተፎካካሪዬን…ምን ትመስል ይሆን …?ቆንጆ ነች አስጠሊታ? ዘናጭ ነች ዝርክርክ..?ንግግር አዋቂ ነች ወይስ ሞዛዛ ዝም ብላ የሀብታም ልጅ.?
አባቴንና ሽማግሌውን አንድ ላይ ጥያቸው የግል ቢሮዬ በመግባት መስኮት ላይ ተለጥፌ ወደታች እያየው ነው፡፡ወደታች ወደ መግቢያው በር…ማንን ነው የምጠብቀው……? ተፎካካሪዬን፡፡ምንድነው እንደዚህ ያስጨነቀኝ……?ምንም ቢሆን ምንም ከደቂቃዎች ቡኃላ ማየቴ እደሆነ አይቀር…ስል አንድ የማውቃት ግን የካምፓኒው ያልሆነች መኪና ስትገባ አየው፡፡ልቤ ትርትር ነው ያለችው፡፡ይህቺን መኪና አውቀታለው፡፡ በቢሾፍቱው የካምባኒው ዝግጅት ጊዜ ፊናን ይዛት የነበረችው አይነት መኪና ነች፡፡ፌናን መጣች ማለት ነው?፡፡በውስጤ ደስታ ሲፈስ ታወቀኝ … መስኮቱን ለቀቅኩና በፍጥነት ቢሮዬን ለቅቄ በመውጣት ሊፍቱን አንኳን መጠበቅ አቅቶኝ ወደታች ወደግራውንድ በደረጃ እየተንደረደርኩ መውረድ ጀመርኩ፡፡ሰራተኞቹ ሁሉ ምን ተፈጠረ እያሉ በአግራሞት ሲመለከቱኝ ብታዘብም ቁብም አልሰጠኝም ፡፡አዎ ታፈቅራኛለች ማለት ነው.? በዚህች ቀን ከጎኔ ልትሆን ከወሰነች ይህን አይነት አሳቢነት ከፍቅር ውጭ ሌላ ሊሆን አይችልም፡፡ምን አይነት ብርሀናማ ቀን ነው…? ፌናን የእኔ ቆንጆ ግራውንድ ወርጄ እሷን ለማየት አይኖቼን ሲቅበዘበዙ ሴትየዋ ከፊት ለፊቴ ገጭ አለች…. የተፎካካሪዬ እናት ወ/ሮ ክብረወርቅ ፡፡ፊቴን እንደጨመዳድኩ ወደእሷ ቀረብኩና ሰላምታ ሰጠዋት…..
‹‹…ትልቅ ሰው ሆነህ የለ እንዴ…? ››በሚል አድናቆት በሞቀ ሰላምታ ምላሽ ሰጠቺኝ..ግራ ገባኝ..፡፡ዙሪያዋን ቃኘው ብቻዋ ነች ፡፡ልጇስ …..?…ተፋላሚዬ የት አለች……..?ደግሞ ፌናንስ …?መኪናዋን ልታቆም ቤዝመንት ገብታ መሆነ አለበት
‹‹ልጆትስ……..?››
‹‹እየመጣች ነው››
‹‹አሪፍ ነው በቃ ይግቡ መጣው ››ብያት አልፌ ወደቤዝመንት ገባው ..ከላይ ያየዋት የፌናን የመሰለቺኘ መኪና በስርዓት ቆማለች፡፡ፌናን ግን የለችም፡፡በየት ጋር አልፋኝ ወደላይ ወጣች፡፡በሊፍት ይሆናል…ወጣውና ዘበኛውን ጠየቅኩት፡፡
‹‹አይ እሷ አይደለችም..እሳቸው ናቸው… አሁን ሰላም ያልካቸው ትልቅ ሴትዬ..መኪናዋ የእሳቸው ነች›› አለኝ..
በቅርብ የተቀጠረ ስለሆነ ሴትየዋን አያውቃቸውም::ደሜ በአንዴ ረጋ…ካልጠፋ መኪና የእኔን ቀልብ ለመረበሽ እንዴት ተመሳሳይ መኪና እየነዳች ትመጣላች?በፊትም ብዙም አልወዳትም አሁን ደግሞ አስጠላችኝ::አይ ማስጠላት እንኳን አላስጠላቺንም ምንም ቢሆን የአባቴ ውሽማ አይደለች..?ግን አናዳኛለች…በጣም..፡፡
አሁን በደረጃ የመውጣቱ ሞራል ስለሌለኝ ጠብቄ በሊፍት ወጣው::ሶስቱም በስብሰባ አዳራሽ ዝግጁ ሆኖ እየጠበቁኝ ነው::ሰዓቱም 5ደቂቃ ብቻ ነው የቀረው::ሰዓት ማክበርም አንዱ መስፈራታቸው ሊሆን ስሚችል ብዬ ቤሮዬ ገባውና ሠነዶችንና ለገለፃ ሚረዱኝን ማቴሪያሎች ሁሉ በፀሀፊዬ አስይዤ ወደ አዳራሹ ገበው::አባቴና አቶ ከበደ ከግራና ከቀኝ ወ/ሮ ክብረወርቅን መሀካል አድርገው አስፈሪ በሆነ ሁኔታ በመደዳ ተቀምጠዋል::የሆነ በሞት ወንጀል ተጠርጥሮ የመጨራሻ ፍርድ ሊሠጡ የተሰየሙ ዳኞች መስለው ታዩኝ::የገዛ አባቴ እራሱ አኮሰታተሩ ይገፋተራል::ከደቂቃዎች በፊት በፈገግታ ሲያበረታታኝ እና ግንባሬን እየዳበሰኝ ሲያጀግነኝ የነበረው አባቴን አልመስል አለኝ::እንዴ ይሄ ሁሉ ጨለማ ፊት ምንድነው …?የድንበር ጉዳይ አደረጉት እኮ..፡፡
….ልጀምር ሰዓቴን ለማየት ሞባይሌን እያወጣው ባለውበት ቅጽበት ስልኬ ጠራ አየውት::ቀጥታ እየተንደረደርኩ ወደውጭ ነው የወጣውት:: ፌናን ነች ፡፡ደወለቺልኝ…፡፡በረንዳ ላይ እደደረስኩ አነሳውት
‹‹አንቺ አለሽ?ምን ሆነሽ ነው ግን..…..?ሰው ይጨነቃል አትይም እንዴ…..?››ወቀሳዬን አዝጎደጎድኩት
‹‹ተረጋጋ..አሁን እኮ መጥቼያለው…››ዘናና ለስለስ ባለ ድምፅ
‹‹የት ነው ያለሽው .. …..?ቢሮ ነሽ ልምጣና ልይሽ…››
‹‹አረ ገና እቤት ነኝ…ከአንድ ሰዓት ቡኃላ እመጣለው…››
‹‹እፎይ በመደወልሽ እና ድምጽሽን በመስማቴ አንዴት ደስ እንዳኝ ልትገምቺ አትቺይም ..››
‹‹ ልፋታችንን አደራ ልልህ ነው የደወልኩት..አሪፍ አድርገህ በሙሉ በራስ መተማመን አቅርብላቸው…ለአንድ ስራአስኪያጅ ከሚሰራው ስራ እኩል ኮሚኒኬሽን እስኪሉም ወሳኝ ነው፡፡ተናግሮ የማሳመንና የመደራደር ብቃትህን ይፈልጉታል::በምታቀርበው:: ሁለት ዲግሪ ስለሌላቸው ዝቅ አድርገህ እንዳትገማታቸው::ከህይወት ውጣውረድ በልምድ ያገኙት በብዙ ዲግሪዎች የሚመነዘር የዳበረ ዕወቀት ባለቤት ናቸው››
‹‹ይሄን እኮ ብዙ ጊዜ ነግረሺኛል ::እንኳን ድምጽሽን ሰማው እንጂ አደርገዋለው…››
‹‹እንደምታደርገው አውቃለው…ከአንድ ሰዓት ቡኃላ እንገናኛለን…››
‹‹እሺ በጣም ነው የማፈቅርሽ ::ጨርሼ ስወጣ ቢሮዬ ወይም በረንዳው ላይ እንደማገኝሽ እርግጠኛ ነኝ››
‹‹እሺ ቻው››
‹‹ስልኬን መዝጋት ብቻ ሳይሆን አጠፋውና በፈገግታ ወደውስጥ ገባው…ቀጥታ ለሶስቱም የተዘጋጀውን ሰነድ ካስረከብኩ ቡኃላ
ፊት ላፊታቸው ቆሜ ወደ ገለፃዬ ለመግባት ጉሮሮዬን አፀዳዳው፡፡በፋካ ፊት…በተረጋጋ ስሜት….በሙሉ የራስ መተማመን…..

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍2
አትሮኖስ pinned «#ፍቅር_ከፈላስፋ ፡ ፡ #ክፍል_ሀያ_ሰባት ፡ ፡ ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ ፡ ፡ #ፍሰሀ ፡ ፡ ብቻ አሁን ከንጋቱ 12 ሰዓት ነው…መኝታዬን ለቅቄ ቢጃማዬን እያወላለቅኩ ወደሻወር ቤት አመራው…የሻወሩን ውሀ ለብ እንዲል አደረግኩና ገባውበት…አዎ ንጹህና ቀለል ብሎኝ መዋል ነው የምፈልገው፡፡ ዛሬ የምለብሰውን ልብስ ከአስር ቀን በፊት ነበር የተዘጋጀው…ሙሉበሙሉ በፌናን ምርጫ በጥንቃቄ ተመርጠው የተገዙ አዳዲስ…»
#ፍቅር_ከፈላስፋ


#ክፍል_ሀያ_ስምንት



ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ



#ፍሰሀ
===
ልዩ የሆነ ቆይታ ነበር፡፡ሶስቱንም ፈታኞቼን እንዳስደመምኮቸው እርግጠኛ ነኝ፡፡መድረኩን በስነስርዓት፤ ባጠናውት እና በተዘጋጀውት መጠን ነበር የተወጣሁት፡፡በመጨረሻ ሁሉም ወ/ሮ ክብረወርቅም ጭምር ቆመው ነበር ያጨበጨብልኝ፡፡እኔም በደስታ ሰክሬ ከወገቤ ሽብርክ ብዬ አመሰገንኳቸው፡፡
ለመውጣት ቸኩያለው ቀልቤ ያለው ፌናን ጋር ነው፡፡እስከአሁን ከቤቷ መጥታ ውጭ በረንዳ ላይ ወይም ቢሮዬ ቁጭ ብላ እደምትጠብቀኝ እርግጠኛ ነኝ፡፡አዎ አይኖቼ መላ እሷነቷን ተርበዋል፡፡ከራሴ በላይ እወደዋለው፡፡ ብዬ የማስበው አባቴ እንኳን ከስድስት ወር ባላይ ተለይቶኝ ሲኖር በዚህ መጠን ናፍቆኝና ተርቤው አላውቅም…
ናፍቆቴ የቱንም ያህል ቢሆን ግን እነሱን ቀድሜ መውጣት በአይን አውጣነት የሚያስፈርጀኝ መስሎ ስለተሰማኝ እንደምንም ስሜቴን ተቆጣጥሬ እየታገስኩ ነው፡፡እነሱ በእርጋታ የሚንቀሳቀሱትን ሽማጊሌውን አስቀድመው እየተጎተቱ ክፍሉን እስኪለቁልኝ መጠበቅ ግድ ሆነብኝ፡፡ይባስ ብሎ አባቴ ወደእኔ መጣ፡፡ተጠመጠመብኝ ፡፡ምን ላድርግ …?መልሼ በተመሳሳይ አቀፍኩት፡፡ለዚህች ቀን አይደል ስንት ወር ሙሉ ሲወተውተኝ የነበረው?እሱ ያልተደሰተ ማን ይደሰታል……?ግን እሱ ያላወቀው እንዲህ መታቀፍ ያለብኝ እኔ ሳልሆን ፌናን መሆኗን ነው፡፡ግድ የለም ..እሱ እኔን ባቀፈኝ መጠን እኔ ደግሞ ከደቂቃ ቡኃላ እሷን አቅፋታለው፡፡.ጭምቅ አድርጌ አቅፋትና ምስጋናዬን አቀርብላታለው፡፡ምስጋናዬን ብቻ ሳይሆን ዛሬ ማታ አፕል አበረክትላታለው፡፡አዎ ጥንት ግሪካዊያን ለሚያፈቅሩት ሰው አፕል ነበር የሚልኩት አንተም የምታፈቅረኝ ከሆነ ከዝግጅቱ ቡኃላ አፕል ላክልኝ የዛን ጊዜ መልሱን ነግርሀለው አይደለ ያለቺኝ?ዋው..ማታ እራት ጋብዛታለው::ከዛ አፕል እሰጣታለው::አፕሉ ውስጥ ደግሞ ቀለበት ይኖርታል::አብረቅራቂ የአልማዝ ቀለበት::ይህንን በማሰቤ ውስጤ ዘላለማዊ በሚመስል ደስታ ተጥለቀለቀ
‹‹በጣም ነው ያኳራኸኝ…እጅግ በጣም ከጠበቅኩት በላይ ጀግና ሆነህልኛል ለካ?አሁን እርግጠኛ ሆነህ ካማፓኒውን በቋሚነት ለመረከብ ተዘጋጅ..››አለኝ አባቴ ሌሎቹ ሊሰሙት በማይችሉት ዝቅተኛ ድምጽ
‹‹እሺ አባዬ አመሰግናለው፡፡››
‹‹ና እንውጣ›› አለኝና ትከሻዬን በኩራት አቅፎ ወደውጭ ይዞኝ ወጣ::በራፍ ላይ እንደደረስን በሃያ ሜትር ርቀት ፌናን ቀድመውን ከወጡት ጋሽ ከበደ እና ከወ/ሮ ክብረወርቅ ጋር ሲያወሩ ለዛውም እየተሳሳቁ ተመለከትኩ
እኔም አባቴም ሳንነጋገር እርምጃችንን እዛው በራፍ ላይ ገታነው::እንዴት አምሮባታል ?ይህ ሁሉ ውበት እንዲህ ጎልቶ እና ፈክቶ የወጣው ከእራሷ ከአፈጣጠር ነው ወይስ ከአለባበሷ…?ልቤ እንደለመደችው ቅልጥልጥ አለች…ግን ከሰዎቹ ጋር የት ተዋውቃ ነው እንዲህ በመፈንጠዝያና በፈገግታ የምታወራቸው……?
‹‹አንተ ተፋላሚህ መታልሀለች::ደግሞ እንዴት ታምራለች……?ልክ እንደእናቷ ››አባቴ ነው በአድናቆትና በስጋት መሀከል በሚዋልል ስሜት የተናገረው…
‹‹አባ እሷ አይደለችም::ይህቺ እኮ የእኔ ረዳት ነች››አረምኩት
‹‹እርግጠኛ ነህ…?ፎቶዋና እኮ እናትዬው ያሳየቺኝ መሰለኝ..ለማንኛውም ና ወደ እነሱ እንሂድ..››አለኝና ተያዘን ስራቸው ደረስን …ፌናን ዞር ብላ እንዳየችኝ ተሸከርክራ ተጠመጠመችብኝ….በጣም እንደናፈቀቺኝ ያወቅኩት ሁሉም እያዩኝ ያለይሉኝታ ልክ እንደ ህጋዊ እጮኛዬ አቅፌ በአየር ላይ ሳንጠለጥላት ነው….
አባቴ ‹‹ክብረወርቅ ልጅሽ ነች እንዴ…?››ብሎ ሲጠይቅ በጆሮዬ ገባ..
‹‹አዎ ልጄ ነች::ፌናን ሰላም በይው…››የሰማውትን መልስ ማመን አቃተኝ….. ምንድነው እየተካሄደ ያለው..?.ከእሷ ሸሸት እልኩና እናትዬው ላይ አፈጠጠኩባት
<<…ምን ተፈጠረ …?በሚል ግራ በተጋባ አሰተያየት ንግግሯን ቀጠለች‹‹እንዲህ ምትግባቡ አይመስለኝም ነበር››ለእኔ ነው የምትለኝ ፡፡
‹‹ፌናን ያንቺ ልጅ ነች…?››አንቱነታውንን እረስቼ የአባቴን ጥያቄ መልሼ ደገምኩ
‹‹አዎ ..ፌናን ልጄ ነች..ምነው …?አልነገረችህም እንዴ……?››
ወደ እሷ ተንደረደርኩና ሁለት ትከሻዋን ጨምድጄ ያዝኳት …ሶስትም ደነገጡ‹‹በጣም ባለጌ ነሽ..በጣም አታለሺኛል..መቼም ይቅር አልልሽም….››
ይሄን ሁሉ ስላት እሷ ምንም እንዳልተፈጠረ በግማሽ ፈገግታ እያደማጠቺኝ ነው…ገፍትሬ አባቴ ትከሻ ላይ ወረወርኳትና ወደቢሮዬ ተንደረደርኩ…
‹‹ምንድነው ነገሩ?ልጄን ምን አደረጋችሁት…?››የአባቴ ድምጽ እየተሰማኝ ነው…ቤሮዬን ገባውና ከውስጥ ቀረቀርኩ.. ቢያንኳኩም ልከፍትላቸው አልፈለኩም..ትንሽ ይብረድለት ብለው መሰለኝ ትተውኝ ዞር አሉ….እኔም ምፈልገው ያንን ነበር፡፡
…….ታንቄበት የዋልኩትን ከረባት ከአንገቴ ፈትቼ ጥዬ ኮቴን አውልቄ በመወርወር ወንበሬ ላይ ቁጭ ብዬ አንገቴን ጠረጳዛ ላይ ደፍቼ አነባው ጀመር::እንዲህ አይነት ለቅሶ ካለቀስኩ ስንት ዓመት እንዳለፈኝ ትዝ አይለኝም::ንፍጤ እስኪዝረከረክ ድረስ ነው ያለቀስኩት፡፡በህይወቴ አንድ ሰው በዚህ መጠን ተጫውቶብኝና አታሎኝ አያውቅም::እንዴ አምኜያት ነበርኮ..?በአድናቆት ፈዝዤያለት አፍቅሬያትና ብዙ ብዙ ህልም አልሜላት ነበር…?እንዴት አንዲህ ትሰብረኛለች?ይህችን ካምፓኒ ለማስተዳደር ብላ……?እኔ እኮ ከካምፓኒው ስራ በላይ ነበር ያፈቀርኳት…
…እያንዳንዷን የሰራዋትን ጥናት ቃል በቃል ታውቀዋለች፤ ምክንያቱም አብረን ነው የሰራነው.፡፡ስለዚህ የእሷ ዝግጅት የእኔን ጥናት አይታና ከእዛ በበለጠና ያንን በሚያጠቃ መልኩ ለማዘጋጀት እድሉን አግኝታለች… .በዛ ላይ ችሎታዋን አውቃዋለው..እና እንዴት ነው ከእሷ በልጬ ይሄን ቦታ የማገኘው…?ተዋረድኩ….፡፡በቃ ሁሉ ነገር አስጠላኝ ::ስራው አስጠላኝ ..ካምፓኒውም አስጠላኝ ..ያፈቀርኮት ልጅ አስጠላቺኝ…ሀገሬም አስጠላቺኝ …፡፡መመለስ አለብኝ…አዎ ወደመጣውበት ሀገር እመለሰላው..ስደት ይሻለኛል..ስራዬን እየሰራው ሶስትኛ ዲግሪዬን ብማር ይሻለኛል..::እንደውም በተጨማለቀ ሀገር የተጨማለቀ ኑሮ ለመኖር ምንድነው እንደዚህ አፈር የሚያስግጠኝ..…?ወሰንኩ…እንባዬን ከጉንጬ ላይ ጠራረግኩ…ኮምፒተሬን ከፈትኩና መጻፍ ጀመርኩ…ለቦርድ አባላቱ ነው::የካምፓኒውን ስራ ስለማልፈልገው ውድድሩ እንዲቀርና ስራውንም በገዛ ፍቃዴ መልቀቄን የሚገልጽ ደብዳቤ …ፕሪንት አድርጌ ፈረምኩበትና ኮቴን መልሼ በመልበስ ወጣው…ሰራተኞቹ ሁሉ ለምሳ የወጡ ቢሆንም ጸሀፊዬ ግን ስጠብቀኝ ነበር….
‹‹አሁን የቦርድ አባሎቹ ሲመጡ ይሄንን ማመልከቻ አስገቢልኝ›› አልኩና በካኪ ፓስታ የታሸገውን ማመልከቻ ሰጠዋት
‹‹አባትህ ደጋግመው ሲደውሉ ነበር…ምሳ እየጠበቅንህ ነው ፤ደውልኝ ብለውሀል…››
‹‹ዝም በይው::ስልኬን ዘግቼዋለው …ከደወለ ወጥቼ እንደሄድኩና እንደማልመለሰም ንገሪው……››
‹‹አንተ ግን ሰላም ነህ…?›ሁኔታዬ ስላላማራት መሰለኝ የጠየቀቺኝ
‹‹ሰላም ነኝ ….አመሰግናለው…››ጥያት ወጣው…..

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
አትሮኖስ pinned «#ፍቅር_ከፈላስፋ ፡ ፡ #ክፍል_ሀያ_ስምንት ፡ ፡ ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ ፡ ፡ #ፍሰሀ === ልዩ የሆነ ቆይታ ነበር፡፡ሶስቱንም ፈታኞቼን እንዳስደመምኮቸው እርግጠኛ ነኝ፡፡መድረኩን በስነስርዓት፤ ባጠናውት እና በተዘጋጀውት መጠን ነበር የተወጣሁት፡፡በመጨረሻ ሁሉም ወ/ሮ ክብረወርቅም ጭምር ቆመው ነበር ያጨበጨብልኝ፡፡እኔም በደስታ ሰክሬ ከወገቤ ሽብርክ ብዬ አመሰገንኳቸው፡፡ ለመውጣት ቸኩያለው ቀልቤ…»
.:
#ፍቅር_ከፈላስፋ





ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ (የመጨረሻ ክፍል)


❤️ፌናን
===
ይሄ እንደሚፈጠር ቀድሞውኑም ጠብቄያለው::ቀድሜ መናገር
ነበረብኝ …ግን ልረብሸው ስላልፈለኩ ነበር እንደዚህ ያደረኩት
::.ሁኔታውን እንዳወቀ አባቱ ትከሻ ላይ ገፍትሮኝ እየተመናጨቀ
ቢሮው ገብቶ ከዘጋ ቡኃላ ሶስቱም ነበር ያፈጠጡብኝ….
‹‹ምንድነው ልጄን ያደረጋችሁት…? ››አሉ አባቱ…..ያው
ያደረግሽው ለማለት ፈልጎ ነው፡፡
‹‹ምንም ያደረኩት ነገር የለም::ግን ተወዳዳሪው እኔ ትሆናለች
ብሎ ስላልጠበቀ ነው የተበሳጨው››መለስኩ
‹‹በዛማ አይበሳጭም::ጥናቱን ሲሰራ ምትረጂው አንቺ ነበርሽ
አይደል…?››
‹‹አዎ …በሙያዬ ፕሮፌሽናል በሆነ ደረጃ
ረድቼዋለው::የማውቀውን ምንም ወደኃላ አላልኩም::ምነው
ጥናቱ አሪፍ አልነበረም እንዴ…?››
‹‹ጥናቱማ ሁላችንንም ያስደመመ እንከን አልባ ነበር…››መለሱ
አባቱ ግራ በተጋባ ስሜት
‹‹ስለዚህ ምንም ያጠፋውት ነገር የለም ማለት ነው››መለስኩ
‹‹ልጄን አባሳጭተሸዋል…የክብረወርቅ ልጅ መሆንሽን አለመናገርሽ
አግባብ ስራ አልነበረም..››በጋለና በሞቀ የንዴት ስሜት
‹‹በቃ ልጄ ላይ አትጩሁባት ..ካልፈለገች አለመናገር መብቷ
ነው::የበደለችው ነገር ከለ ወይም ጥናቱ ላይ ያሳሳተችው ነገር
ካለ ለቦርዱ አቤቱታውን ማቅረብ ይችላል…››እናቴ ተንዘረዘረች
‹‹በቃ አቀዝቅዙት..አሁን እሱ ትንሽ ይረጋጋ እኛ ወደ ምሳው
እንሂድ››አቶ ከበደ ናቸው የተናገሩት
‹‹ሂዱ እኔ ከልጄ ጋር ነው የምበላው ..ጠብቀዋለው››
‹‹ተው አንተ ደግሞ ሰው ሚልህን ስማ ..ትደውልላታለህ ፡፡ቀለል
ብሎት በወጣ ሰዓት ይቀላቀለናል..››ብለው አሳመኑትና የቢሮውን
ህንፃ ለቀን ወጣን..እኔ ግን አብሬያቸው ወደ ሆቴል አልሄድም
አልኩ::ቢቆጡኝም አለሰማዋቸውም::ብቻዬን መሆን ነው
የፈለኩት::የሰራውትን ነገረ ሁሉ አምኜበትና አስቤበት ቢሆንም
ፍሰሀን የመከፋት መጠን ባየው ጊዜ ከፋኝ::ይሄን የመከፋት
ስሜት ደግሞ ብቻዬን ነው ማጣጣም የምፈልገው….
እንግዲህ ለአምስት ሆነን ልንቋደስ የነበረው የምሳ ፕሮግራም
ወደ ሶስት ሰው ዝቅ አለ ማለት ነው፡፡
ሰዓቱ ከቀኑ 8፡10 ሆኖል ፡፡አሁን እራሴን አረጋግቼ ቅድመ
ዝግጅቴን ጨርሼ ሶስቱ የቦርድ አባላት ፊት ለፊት
ቆሜያለው::የጥናት ወረቀቴን ከቦርሳዬ አወጣውና ለሶስቱም
አደልኩ::ሶስቱም ላይ ግራ መጋባት አየው::ሽማግሌው አቶ ከበደ
ግራ ገብቷቸዋል::የፍሰሀ አባት ፈገግ አሉ ::እናቴ ፊቷን
ጨመደደች እና እንደውም ይባስ ብላ በንቀት መልክ ከ10 ገጽ
የማይበልጠውን የጥናት ወረቀቴን በሁለት ጣቷ አንጠልጥላ
እያወዛወዘች‹‹በቃ››አለቺኝ
‹‹ምኑ…?››
‹‹ለወራት ውስጥ ያዘጋጀሽው የመወዳደሪያ የጥናት ወረቀትሽ
ይሄው ብቻ ነው…?››ምን ታርግ መቶ ገፅ ሊሞላ ትንሽ ገጽች
ከሚጎድሉት የፍሰሀ የጥናት ወረቀት ጋር ስታነፃፅረው ከወዲሁ
ሀሞቷ ፈሶ ነው፡፡
‹‹አንዴ የቀረበው ቀርቦል…. እንስማው››አለ የፍሰሀ አባት
ጨፍግጎት የነበረው ስሜት ለቆትና ኩርፊያውንም ረስቶት..
‹‹እሺ ቀጥለላው.. ››ስል..በራፉ ተንኳኳ::ፍሰሀ ሊበጠብጥን
መጣ ይሆን እንዴ……?ወዲያው በሀሳቤ የተሰነቀረ ክፉ ሀሳብ
ነበር
‹‹ይቅርታ… ››አልኩን ሄጄ ስከፍት የፍሰሀ ፀሀፊ ነች
‹‹ይቅርታ ይሄን ለእነሱ ልሰጥ ነበር››አለቺኝ የሆነ ካኪ ፖስታ
አንከርፍፋ
‹‹አንጪ እኔ ልስጥልሽ››
እንደማቅማማት እያለች ሰጠቺኝ..በራፉን ዘጋውና ሂጄ ለጋሽ ከበደ
ሰጠዋቸው..
‹‹ምንድነው…?››
‹‹እኔ እንጃ የፍሰሀ ፀሀፊ ነች ያመጣችው››
<<.አባትዬው ከጋሽ ከበደ እጅ ፓስታውን መንጭቀው ተቀበሉትና
ሸረከቱት …ከዛ ለብቻቸው ያነቡት ጀመር…ምን ይፈጠር ይሆን…?
ብለን ሌሎቻችን በንቃት እየጠበቅን ነው ‹‹ያው ደስ ይበልሽ
ያለውድድር አሸንፈሻል››አሉኝ አንብበው እንደጨረሱ እኔ ላይ
አፍጥጠው
‹‹ምንድነው እሱ…?›› ጋሽ ከበደ ናቸው ጠያቂው
‹‹ያው ስራውን አልፈልግም የሚል ማመልከቻ ነው ያስገባው…
መቼስ ይሄንን አይነት ስውር ብልሀት ከእናትሽ ነው
የወረሺው::ሳትፋለሚ በብልጠት ማሸነፍን ››
‹‹ሰውዬ ምን እያወራህ ነው…?››እናቴ ነች በእሱ ልክ ግላና
እየተንዘረዘረች ዘራፍ ተደፈርኩ በሚል ሰሜት የተናገራቸው
‹‹በቃችሁ…››እኔ ነኝ መሀከል የገባውት..‹‹ይሄ የልጆች ጫወታ
አይደለም::እናንተ በመሀከላችሁ ያለውን የግል ንትርክ በአኔ
አሳባችሁ ማወራረድ አትችሉም::እኔ የተዘጋጀውበትን ሳለቀርብ
ከዚህ አልወጣም::ሳልወዳደርም ማሸነፍ የምፈልግ ሰው
አይደለውም::ምክንያቱም የፍሰሀ አባት አንድ የማያውቁት ነገር
ያለ ይመስለኛል… እኔ የእናቴ ልጅ ብቻ ሳልሆን የአባቴም ልጅ
ነኝ::አባቴ ደግሞ ገነትም ቢሆን በአቋራጭ እንድገባ አድርጎ
አላሳደገኝም…. ››
ጋሽ ከበደ በዛ እርገታቸው መሀከል ገቡ‹‹እወነቷን ነው…የፍሰሀን
ጉዳይ ቡኃላ እንዴት ማድረግ እንዳለብን እንመክራለን::ፕሮግራሙ
ግን በዕቅዱ መሰረት መቀጠል አለብን::ትልልቅ ሰዎች አይደለን
እንዴ…? ስሜታዊ መሆን አሁን ምን ይረባል……?››
‹‹መልስ እንዲመልሱ እድል ሳልሰጣቸው ቀጠልኩ
‹‹አመሰግናለው::ምን አልባት ያቀረብኩት የጥናት ወረቀት መጠን
አነስ ያለች በመሆኗ ከተመደበልኝ ጊዜ ውስጥም ስልሳ ፐርሰንቱን
ብቻ ተጠቅሜ ሙሉውን ዝግጅት ለማጠናቀቅ
እሞክራለው::ስለዚህ ሁላችሁም ምናባችውን ሰብሰብ አድርጋችሁ
በትኩረት እንድትከታተሉኝ እየጠየቅኩ ቀጥታ ወደ ገለፃዬ
እገባለው፡፡››
ካምፓኒው የተቋቋመበት ዓላማ ምንድነው…?ለካምፓኒው
ባለቤቶች ደለብ ያለ ትርፍ በየዓመቱ ማስገኘት?መቶና ሁለት መቶ
ለሆኑ ዜጎች ቋሚ ስራ መፍጠር .. …?ከ5መቶ እስከ 1 ሺ
ለሚሆን ጊዜያዊ ሰራተኞች የስራ እድል መፍጠር..…?ለመንግስት
ግብር በማስጋባት የዜግነት ግዴታን መወጣት…? በቃ ይሄ ነው
…..…?
እርግጥ ሶስት ሰዎች ያቋቋሙት ካምፓኒ እንዲህ ውጤታማ ሆኖ
በዚህ መጠን ለሌሎችም ሆነ ለሀገር ጥቅም ከሰጠ አስደሳች
ነው…ስኬታማ የሚያሰኝ ነው…ግን በእኔ አስተያየት ተራ ስኬትና
ተራ አላማ ነው፡፡….እኔ ይሄ ካምፓኒ ልዩ እና የማይቻለውን ነገር
አስችሎ ለመላ ሀገሪቱ እንዲያሳይ ነው የምፈልገው…
ኢትዬጵያ 20 ሚሊዬን ዜጎቾ ከድህነት ወለል በታች የሚኖሩባት
ሀገር መሆን ነበረባት…?ዘወትር በስደት በየባህሩ የምናልቅ
ህዝቦች መሆን አለብን…? ፡፡ይሄ ቁጭት በውስጤ አለ ፡፡ከዚህም
ቁጭት የተመዘዙ የራሴ የሆኑ ሁለት እቅዶች አሉኝ፡፡አንደኛ
በሚቀጥሉት አስር አመት ውስጥ ውጤታማ የቢዝነስ ሰው
በመሆን ሀገሬንና ህዝቤን መርዳት …ሁለተኛ ከአስርአመት ቡኃላ
በቢዝነስ ያገኘውትን እውቅና እና ጥበብ ይዤ ወደፓለቲካ
መግባት እና የዛሬ ሀያ አመት ከተራዘመም ሀያ አምስት አመት
ድረስ ይህቺን ሀገር መምራት …
‹‹ማለት…?››አለች እናቴ በአግራሞት..
‹‹ጠቅላይ ሚኒስቴር መሆን…እና ይህን የሀብት ምንጫችሁ ብቻ
ሳይሆን የስማችሁ መጠሪያ የሆነውን ካማፓኒያችሁን የምፈልገው
መጀመሪያ ለራሴ አላማ ነው…፡፡ካፓኒውን በተለየ መልኩ
ውጤታማ አድርጌ ለዚህች ሀገር የቢዝነስ ሞዴል እንዲሆን
በማድረግ የራሴን ስም መገንባት::ያንን ማድረግ ከቻልኩ
የእናንተን ፍላጎት ብቻ ሳይሆን የራሴንም ህልም ነው
የማጨልመው…
እና እንዴት አድርገሽ ነው የተለየ ካምፓኒ የምታደርጊው……?.በእኔ
እምነት በአሁኑ የካማፓኒ አካሄድ ለሀገሪቱ እድገት እየተጋለ እና
የራሱን አስተዋፅኦ እያበረከተ ነው? አዎ ትክክል ነው…
በተቃራኒውን ለሀገሪቱ ውድቀትም በተመሳሳይ አስተዋጽኦ ቀላል
አይደለም…
ንግግሬን ገታ አድርጌ የሶስቱንም ፊት ሳይ ልጅቷ አብዳለች እንዴ
👍8
እያሉ ይመስላል…

በ19 17 ዓ.ም ሀገሪቱ 3.13 ቢ . ዶላር ምርት ለውጭ ገበያ
ስታቀርብ ወደ ውስጥ ያስገባችው ምርት ደግሞ 16.29 ቢሊዬን
ዶላር ነው፡፡ ምን አይነት ኪሳራ ውስጥ ያለች ሀገር መሆኗን እዩልኝ
..ሀገሪቷ ሰርታ ብቻ ሳይሆን ተበድራም ፤ለምናም የሰበሰበችውን
ዶላር ነው እኛ እያወጣን የሚያሰሰፈልገውንም የማያስፈልገውንም
ኮተት ከቻይና እና ከህንድ እየሰባሰብን አምጥተን ለህዝቡ
የምናድለው፡፡እስቲ ገጽ አራት ላይ ክፈቱና የምናስመጣቸውን የዕቃ
ዝርዝሮች ተመልከቷቸው፡፡ከውስጣቸው ምን ያህሉ ነው የግድ
አስፈላጊ የሆኑት ዕቃዎች …?አንዳንዶቹ የሚያሳፍሩ ናቸው….
..…የማንጎ ጁስ ፤የብርቱካን ጁስ ፤ የመንደሪን ጁስ ዶላር
ከፍለን ከሰውዲ እናስመጣለን፡፡ኑግ፤ተልባና ሰሊጥ
እያመረትን..በተጨማሪም የትየለሌ የምናመርትበት መሬት እያለን
ዘይት ዶላር ከፍለን እናስመጣለን……የህፃናትም ሆነ የአዋቂዎች
ልብስና ጫማ ዶላር እየከፈልን እናስመጣለን፡፡ ቆዳውም ጥጡም
በሀገራችን መመረት እየተቻለ….ሌላ የሴቶች መዋቢያዎች
፤አርቴፊሻል ፀጉር፤ አርቴፊሻል ጡት፤ አርቴፊሻል
መቀመጫ፤ሊፒስቲክ ፤ቻፒስቲክ ፤ቅባቶች ፤ዶላር ከፍለን
እናስመጣለን፡፡
ሚሊዬኖች ከድህነት ወለል በታች በሚኖሩባት ሀገር በመከራ
የሚገኘውን ዶላር የምንጠቀምበት አግባብ አይታችሁታል …?ለዚህ
ደግሞ ተጠያቂ ከሆኑት የመንግስት ፓሊስ ቀጥሎ ካምፓኒያችን
ከተጠያቂዎቹ ውስጥ አንዱ ነው፡፡ቢያንስ የሚያስገባቸውን ዕቃዎች
እንኳን ምን ያህል ትርፍ ያስገኚልኛል ብቻ በሚለው መስፈርት
ሳይሆን መሰረታዊ ነገር ሆኖ በሀገሪቱ መመረት ያልቻለው የትኛው
ነው ብሎ በመምረጥ ዶላሩን እንዴት ነው ለሀገሪቱና ለህዝቡ
ወሳኝ ለሆነ ነገር መጠቀም የምችለው…? የሚለውን ማሰብ
ነበረበት…ቢያንስ እንዲህ ማድረግ ይችል ነበር፡፡.
እና ካምፓኒው የውጭ ሸቀጦችን ከየሀገራቱ እያስመጣ በሀገሪቱ
ማሰራጨት ብቻ ሳይሆን ወሳኝ የሆኑትን ምርቶችንም በማምረት
ወደውጭ መላኩ ላይም እንዲሳተፍ እፈልጋለው…
ስለዚህም ካምፓኒው በሁለት ይከፈላል ወይም አሁን ባለው ላይ
ሌላ እህት ካምፓኒ ይመሰራታል… አሁን ያለውን ካምፓኒ
የምናስመጣቸውን ዕቃዎች ዓይነት ብቻ በማስተካከል ወይም
በመምረጥ በቀረበው ዓዲስ ዕቅድ መሰረት ፋሰሀ እንዲመራው
ሙሉ ድጋፌን እሰጠዋለው….
የሚቋቋመውን እህት ኩባኒያ ደግሞ እኔ መምራት ፈልጋለው…ይሄ
እህት ኩባኒያ ሁለት ስራ ነው የሚሰራው..አንድም በየአመቱ አንድ
ወይም ሁለት ምርቶችን ሀገር ውስጥ ከተቻለ የሀገሪቱን ፍጆታ
በሚሸፍን መጠን ካለሆነም በሚያስመጣው መጠን ፍብሪካ
በማቋቋም እንዲያመርት ማድረግ……ለዚህም እንዲረዳ
ካምፓኒው ከሚያገኘው አመታዊ ትርፍ ቢያንስ 75 ፐርሰንቱ
ወደአዲሱ ክማፓኒ ፈሰስ ማድረግ ይጠበቅበታል…፡፡ከውጭ
ኩባንያዎች ጋር ያለውን ግንኙነት በመጠቀም እና እነሱን
በማነጋገር እና በማሳመንም ያንን እንገዛቸው የነበረውን ዕቃ አገር
ውስጥ ከተቻለ አብረውን በጥምረት እንዲያመርቱ ካልሆነም
በራሳቸውም ሙሉውን ኢንቨስት አድርገው በእኛ ካምፓኒ
እንድናከፋፍልላቸው መስራት አለብን.(.ምክንያቱም በዶላር ገዝተን
በባህር አጓጉዘን በማምጣት ከምናከፋፍል እዚሁ እንዲያመርቱ
አሳምነናቸው በብር እየገዛናቸው በብር ብናከፋፍል ይህቺን ሀገር
በቀጣይነት ከቀውስ ለመታደግ የራሳችንን ሚና መጫወት
እንችላለን…..)
ሌላው እርግጠኛ ነኝ ሶስታችሁም በቂ ብር ለዛውም በዶላር
ዱባይ ወይም ሌላ ውጭ ሀገር አላችሁ ብዬ አስባለው…ያንን ብር
በንጽህ ንግድ ብቻ ያገኛችሁት ነው ብዬ አላስብም ፡፡ከሆነም ጥሩ
ነው..ግን በምንም ተገኘ በምን ውጭ ማስቀመጡ ፌር
አይደለም..
… ለምሳሌ እማዬ .. ያለውሽ ልጅ እኔ ብቻ ነኝ፡፡እኔ ደግሞ እድሜ
ዘመኔን እዚህችው ሀገር ኖሬ መሞት ነው የምፈልገው፡፡ስለዚህ
ለማን ብለሽ ነው ሰው ሀገር ያን ሁሉ ብር ያሰቀመጥሺው..?ነገ
እኔ ልጅሽ ልመራት እቅድ ያለኝ ሀገር ነች…ግን እናንተ እና
የእናንተ ትውልድ በፓለቲካም ሆነ በኢኮኖሚ አሻጥር
ጭምልቅልቋን ያወጧችሆትን ሀገር እኔ ልጅሽ እመራለው ብዬ
ተረክቤ ምን ያህል እንደምሰቃይ ታውቂያለሽ……?ያ ገንዘብ ደግሞ
እውነቴን ነው የእናንተ ብቻ ይመስላችሆል እንጂ የእናንተ ብቻ
አይደለም ፡፡የሀገርም ንብረት ነው…ሀገር አደገች የሚባለው
የእያንዳንዱ ሰው እድገት ተደምሮ ነው..ስለዚህ ሶስታችሁም
ቢያንስ በተለያየ ስጋት ወደውጭ ያሸሻችሁትን ወይም በየቤታችሁ
የቀበራችሁትን ብር ታመጡና ለዚህ ሲስተር ካምፓኒ ማቋቋሚያ
ትሰጡኛላችሁ ማለት ነው፡፡ከዚህ በላይ ገናዘብ ካስፈለገንም
ከመንግስት በአግባቡ እንበደራለን…፡፡
ሶስቱም እርስ በርስ ተያዩ….
እኔ ቀጠልኩ‹‹ ….እና ቀስ በቀስ የምናስመጣቸውን ዕቃዎችን
በተለይ የምግብ ዘይት፤ ሳሙና ፤ወረቀት ፤ጅውሶችን .፤
፤እስኪሪብቶ፤መድሀኒቶች፤ወዘተ ወደ ማምረት እንሸጋገራለን
ሌላ ከዚህ ካምፓኒ ውስጥ አያይዘን የምንሰራው ስራ አለ፡፡
ከአመታዊ ትርፉ እስከ20 ፐርሰንት ተመድቦ በዜጎች ላይ
በተለይም በህፃናትና በታዳጊዎች ላይ የአመለካከት ስራ መስራት፡፡
ለዛም እንዲረዳን የቴሌቪዝን እና የሬዲዬ የአይር ሰዓት ተከራይተን
በመደበኛ ሁኔታ እንሰራለን፡፡በሌላ በኩልም በፊልሞች በስነጽሁፍ
፤በየትምህርት ቤቶችም ጭምር እንሰራለን ..ይሄ ጉዳይ ከሀገር
መውደድን ጋር ቀጥታ የተገናኘ ነው፡፡ሁሉምን ኢትዬጵያዊ ሲጠየቅ
‹‹ ሀገሬን ወዳለው›› ይላል፡፡እንዴት ነው የምትወደው …?መልስ
የለም…ሀገርን መውደድ እያንዳንዱን የሀገር ምርትን መውደድንም
ይጨምራል …አንድ ሙሽራ ቤት ጥሎሽ ሲመጣ እስኪ ታዘብ…
ጫማው ከኢንግላንድ ነው….ጭብጨባው ልዩ ነው….ቀሚሱ
ከእንግሊዝ …ሽቶው ከፈረንሳይ….ሲባል ሁሉ በኩራትና
በፈንጠዝያ ነው፡፡ ከውጭ ሊገኝ የማይችለውን ጥበብ ቀሚሱን
እንኳን ከኢትዬጵያ ነው ማለታቸው ቅር ሚላቸው ሰዎች አሉ ..ይሄ
ደግሞ ከጭብጨባው ማነስ ያስታውቃል፡፡እስከመቼ ነው
የኢትዬጵያ ነገር ሁሉ የማያምር እና የማያስከብር አድርገን
እንገልፀዋለን..…? እንደው ቅድሚያውን ወስደን መስዋዕትነትም
ቢሆን ከፍለን ካላከበርነው ሌላው ሀገር እንዴት እንዲያከብርልን
እንጠብቃለን…?
የውጭ ዕቃ መጠቀም፤ የውጭ ልብስ መልበስ የተሻለ ሰው
ክራይቴሪያ እንደሆነ በማህበረሰባችን በከፍተኛ ሁኔታ ይታመናል፡፡
ይሄንን ስነልቦና ይዘን ደግሞ አስፈላጊ ምርቶችን ሁሉ በሀገር
ውስጥ ማምረት ብንችል እንኳን ምን አልባት ጎረቤት ሀገሮች
ወስደን ካልሸጥን በስተቀር የሀገር ውስጥ ገበያ ማግኘታችን
ያጠራጥረኛል..እና እኛ የምናመርታቸው ማንኛውን ዕቃዎች
ከውጭ እናመጣቸው ከነበሩት ጋር ሲሆን በተሸለ ጥራት ያላቸው
ከላሆነም ግን ተፈካካሪ በሆነ መልኩ አምርተን በተሸለ ዋጋ
ማቅረብ..ህብረተሰቡም ይሄን በሀገር የተመረተ ምርት መግዛቱ
የፈለጉትን ዕቃ ከመግዛት በላይ ትርጉም እንዳለው በማወቅ ፤
ተጨማሪ ጋቢ ለሀገሩ እያስገኘ መሆኑን በማሰብ እንዲገዙ
ማድረግ…ሁለቱንም በጥምረት መስራት አለባት
እስኪ. በሀገራችን ያሉትን ህንዶችንም ሆነ ቻይኖችን
የሚለብሱትን ልብስ እና ሚጠቀሙትን እቃዎች ተካታትላችሁ
ተመልከቱ…አማራጭ ካላጡ በስተቀር ከሀገረቻው ምርት እኩል
የሚያወዳድሩት ምንም አይነት ምርት የለም የሁለት ብር ዕቃ
ብትሆን እንኳን የሀገራቸውን ዕቃ መግዛት የዜግነት ግዴታን
እንደመወጣት እንደሆነ በደንብ ግንዛቤው አላቸው
ሀገር መውደድ ምንድነው.…?እኛ ማንኛውንም ምርት በታማኝነት
ጥራቱን በጠበቀ መንገድ ማምረት ከዛም ዋጋ ስንተምን
በተገቢውና ስነምግባር ባለው መልኩ መተመን ምን አልባት
ተመሳሳዩን ዕቃ ከውጭ እምጥተን ብናከፋፈል ልናገኘው
👍1
ከምንችለው ትርፍ በግማሽም ያነሰ ሊሆን ይቻላል የምናገኘው…
ግን ምንጎናፀፈው የመንፈስ ልህልና እና ለአገር የምንበረክተው
አስተዋጽኦ መተኪያ አይኖረውም፡፡ገዥውም ያንን በሀገር
የሚመረተውን ምርት ገበያ ላይ ሲያገኝ መቶ ፐርሰንት እንኳን
እርካታ ባይሰጠው ጉዳዩ የግለሰብ ምርትን የመግዛት ጉዳይ ብቻ
ሳይሆን የሀገርንም ምርት የመግዛት እና ያለመግዛት ጉዳይነው
ብሎ የእናት ሽሮ ዘይት ቢያንሰውም ያው ከእናት እጅ የሚፈሰው
ወዘና በራሱ እርካታ አለውና የእየገዛ ማበረታታት…
እና ይሄንን አዲስ ሲስተር ካምፓኒ…እንደእዚህኛው ትርፋማ ብቻ
እንዲሆን አትጠብቁ እንደአንዱ ሞዴል ኤን.ጂ.ኦ ቁጠሩት…ከዛ
ሚለየው የምንጠቀምበትን ብር በእርዳታ መልክ ሰብስበን ሳይሆን
ሰርተን ማግኘታችን ብቻ ነው፡፡ከዛ ውጭ ከውጭ የሚመጡትን
ምርቶች በተለይ ከግብርና ጋር ንክኪ ያለቸውን በእኛው በማምረት
ሆነ በሌሎች መሰል ድርጅቶች ሚመረቱትን ምርቶችን የመጠቀም
ባህልን ስር ነቀል በሆነ መልኩ በህብረተሰቡ ውስጥ ማስፈን፡፡
ይህ የሶስት ወይም የአራት አመት ስራ አይደለም አስር ሃያ አመት
ሊፈጅ ይችላል፡፡እኔ ወደፊት የምመራት ሀገር ቤት ያሉት አይደለም
በአለም ዙሪያ ያሉ ዲያስፖራ የሆኑ የኢትዬጳያ ልጆች
ሜድ.ኢን.ኢትዬጵያ የሚል ማርክ ያለው ምርት ለመግዛት ሱፐር
ማርኬት ከሴፐር ምርኬት ሲያማርጡ ማየት የተለመደ እና የእለት
ተግባር እንዲሆን ነው የምፈልገው ….
ሌላው ፡፡ባለኮከብ ሆቴሎችን ተዎቸው…ትንሽ ገንዘብ ያለው ነጋዴ
እያዳንዱ የቤቱን ፈርኒቺር የሚያስመጣው ከውጭ ነው..የእኛ ቤት
ሰፋ የምግብ ጠረጵዛ ፤ኪችን ካቢኔት ከቻይና ነው ማሚ
ያስመጣችው፡፡.ግን ለምን …?የተለየ ጥራት ስላለው?
አይደለም..፡፡ለጉራ ነው…፡፡ስለዚህ መንግስት እንደዚህ አይነት
አላስፈላጊ ግዢዎችን ወይ ቀረጥ በመጨመር ወይ ደግሞ በሌላ
ዘዴ እንዲቀሩ ወይም እንዲቀንሱና የሀገር ውስጥ አምራቾች
እንዲበረታቱና እዲስፋፉ ማድረግ በዘላቂነት እንደሀገር
የሚጠቅመን ነገር ነው…….
ከውጭ የምናስገባቸውን ነገሮች በየአመቱ እየቀነሱ
የምንሸጣቸው ደግሞ እየጨመሩ መሄድ አለባቸው…ከምንሸጠው
በላይ መግዛት ኪሳራ ነው፡፡በኪሳራ እየኖሩ ደግሞ ከድህነት
መውጣት አይችልም፡፡በድህነት ውስጥ ያለ ማህበረሰብ ደግሞ
በሌላው ማህበረሰብ አይከበርም….፡፡ለሆዱ ሲል ስብዕናውን
ይሸጣል..፡፡ለማግኘት ሲል ክብሩን ያዋርዳል…፡፡የሰው ሀገር ገረድ
ይሆናል…፡፡እና እኔ ለግሌ ስኬት ወይም ለካምፓኒው ስኬት ብቻ
አይደለም መስራት የምፈልገው፡፡ያ ግንጥል ጌጥ ነው..፡፡
እንደህዝብ ታላቅ ወደነበርንበት ማማ መልሰን መውጣት አለብን፡፡
እንደሀገርም ታሪካችን ወደሚተርከው የክብር ሀዲድ ላይ መሳፈርና
በዛም ፀንተን መጓዝ አለብን፡፡ለዛ የቻልኩትን ማድረግ ነው
እቅዴ…
‹‹ጨረስኩ..አመሰግናለው››
ለተወሰኑ ደደቃቃዎች ሶስቱም በድን ሆነው ፀጥ አሉብኝ…ግራ
ገባኝ …፡፡እንዴ እስከአሁን ያወራውት አልገባቸውም እንዴ……?
እግዜር ይስጣቸው ጋሼ ከበደ መናገር ጀመሩ…ወይኔ እያለቀሱ
ነው…፡፡ምን ተበለሻ…..…?
ማህረባቸውን ከኪሳቸው አውጥተው አይናቸውን እያበሱ…‹‹ይቅርታ
ስሜቴ ተነክቶ ነው…ልጅ አለመውለዴ እና እንደ እናንተ
አለመታደሌ እንደዛሬ አጥንቴ ድረስ ዘልቆ ጠዝጥዞኝ አያውቅም ፡፡
በእውነት ሁለታችሁም እነዚህን የመሰሉ በባለብሩህ አዕምሮ
ልጆች ስለወለዳችሁ ፤ ወልዳችሁም ለእራሳችሁም ሆነ
ለሀገራቸው እንዲተርፍ አድርጋችሁ ስላሳደጋችሆቸው ልትኮሩ
ይገባል፡፡ልጄ ቅድም ከፍሰሀ ጋር በተፈጠረው ጭቅጭቅ የልሆነ
ነገር የሰራሽ መስሎ ስለተሰማኝ በውስጤ ደስ ማይል ነገር
እየተሰማኝ ነበር፡፡አንቺ ግን በጣም የምትገርሚና ጉድ የሆንሽ ልጅ
ነሽ፡፡የእኔን መቶ ፐርሰንት ድጋፍ እንዳለሽ ቃሌን አሁኑኑ
ስጥሻለው፡፡ከዛሬ ጀምሮ ለእኔም ልጄ ነሽ..ነይ ሳሚኝ›› አሉና
እጃቸውን እንደክንፍ ዘረጉልኝ…ተንደርድሬ ጉያቸው ገባው፡፡
መጨመጩኝ..እናቴ ተቀበለቺኝ…የፍሰሀ አበትም ከምጠብቀው
በላይ ተደስቶ ትከሻዬን በመነቅነቅ..‹‹እወነትም የእናትሽ ብቻ
ሳይሆን የአባትሽም ልጅ መሆንሽን አሁን ተቀብያለው፡፡››አሉኝ
ቅድም በጎን ለተናገሩኩት መልስ መሆኑን ነው…
‹‹ስለዚህ ከፍሰሀ ያስታርቁኛል ማለት ነው…?፡፡››
‹‹በሚገባ እንጂ…እናትሽ ብትፈቅድ እንደውም አሁኑኑ አብረሺኝ
ወደእኛ ቤት ብንሄድ…?››ያላሰብኩትን ሀሳብ አቀረቡ
‹‹እንሄዳለን…እማ ይቻላል አይደል?››ወደእናቴ ዞሬ በመለማመጥ
ጠየቅኳት
‹‹አይ ብቻሽንማ አልክሽም››ውይ ብቻሽን ማለት ምን ማለት
ነው…? እሷም አብራኝ መሄድ አማራት እንዴ…? በውስጤ
ያጉረመረምኩት ሀሜት ነው፡፡
‹‹እንደውም ሁላችንም ለምን ወደእኛ ቤት እንሄድም እና
የልጆቻችን ስኬት አናከብርም..…?አቶ ከበደ እርሷም ጭምር››
‹‹አረ እኔ ይቅርብኝ..››
‹‹ግድ የሎትም..››
እያንገራገሩ ተስማሙ..ሁላችንም ተከታትለን.ወደ እነ ፍሰሀ ቤት…
እናገኘው ይሆን……?ይቅር ይለኝ ይሆን….…?የወደፊታችንስ እንዴት
ነው የሚቀጥለው፡፡…?

💫ተፈፀመ💫

ስለተከታተላችሁኝ አመሰግናለው🙏
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍2🤔1
አትሮኖስ pinned «.: #ፍቅር_ከፈላስፋ ፡ ፡ ፡ ፡ ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ ፡ #ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ (የመጨረሻ ክፍል) ፡ ❤️ፌናን === ይሄ እንደሚፈጠር ቀድሞውኑም ጠብቄያለው::ቀድሜ መናገር ነበረብኝ …ግን ልረብሸው ስላልፈለኩ ነበር እንደዚህ ያደረኩት ::.ሁኔታውን እንዳወቀ አባቱ ትከሻ ላይ ገፍትሮኝ እየተመናጨቀ ቢሮው ገብቶ ከዘጋ ቡኃላ ሶስቱም ነበር ያፈጠጡብኝ…. ‹‹ምንድነው ልጄን ያደረጋችሁት…? ››አሉ አባቱ…..ያው…»
#ሸሌ_ነኝ


#በሕይወት_እምሻው

"ነይ እዚህ ጋር ! ልብስሽን አውልቀሽ ውስጥ ሳትገቢ...ብርድ ልብሱ ላይ ተኚ" ሲለኝ፣ ልማድ ሆኖብኝ መግደርደር ዳድቶኝ ነበር።

ድሮ፤ ልጃገረድ እንዳለሁ ግዜ መሽኮርመም። ሰው እንጂ ሴት ያልሆኑኩ መስሎኝ፣ ሥጋ ሸጬ እንጀራ ልገዛ ያልመጣሁ መስሎኝ።

አንገቴን እንደሰበርኩ ወደ አልጋው ሄድኩ ሲያገኘኝ እሄድ እንደነበረው አይደለም አካሄዴ።ሰበር ሰካ የለውም፣ ዕዩኝ ዕዩኝ የለውም፣ ተገዝቶ ወደ ሚታረድበት ቦታ እንደሚሄድ በግ ነው አካሄዴ።

ገዥዬ የማያውቀኝ፣ ሰው ፊት ልብሴን ሳወልቅ የመጀመርያዬ እንጀሆነ አያውቅም።

ገዥዬ፣ በገንዘብ ተገዝቼ ከወንድ ለመተኛት ስመጣ የመጀመርያዬ እንደሆነ አያውቅም።

ገዥዬ፣ ለዚህ ስራ ድንግል እንደሆንኩ አያውቅም።

ልብሴን ማውለቅ ሳልጀምር እየፈራው፣ "ይቅርታ....መብራቱን ታጠፋው?" አልኩት።

ዞር ብሎ ዐየኝና፣ "ሃሃ...ሃ! ታሾፌያለሽ እንዴ.? ለምንድን ነው የማጠፋው...? አለኝ። ይስቃል።
ፈራሁ ብለው አያምንም። በሰቀቀን ዝም ብዬ ማውለቅ ጀመርኩ። የአልጋው ጫፍ ላይ ኩምትር እንዳልኩ ድንገት እስካሁን መኖሩን ያላወኩት ብርድ አንዘፈዘፈኝ። ሳል ጀመረኝ።

ይሄን ግዜ ሰውየው ዞር ብሎ ዐየኝና ፤ "ምነው.. ብርድ.. ቲቢ.. ምናምን አለብሽ እንዴ?" አለኝ።

"አይ...በርዶኝ ነው...አያመኝም...አሁን በርዶኝ ነው..." ብዬ ብርድ ልብስ ውስጥ ገባሁ።

"ኖኖ!...ከላይ ሁኚ...አትግቢ..." አለኝ ቶሎ ብሎ ፣ ቀጭን ትዛዝ ነበር።

እምቢ ብዬ መሄድ እንደማልችል ማወቁ አስከፋኝ። እሺ ብዬው ስለመጣሁ እምቢ ብዬ ስለማልሄድ እርግጠኛ መሆኑን ሳውቅ ከፋኝ። ከነሳሌ ከብርድ ልብስ ወጣሁ። መጥቶ አጠገቤ ተኛ። ሰውነቴ በፍርሃት ተንዘፈዘፈ። ነውስጥ ሱሪ ብቻ ሲቀረው ዕርቃኑን ነው።

እግዜር በሚያውቀው፣ ከማላውቀው ሰው ቤት ለማደር መምጣት አልፈለግኩም ነበር።

የማላውቀው ሰው እጁቹን ጭኖቼ መሀል አስገብቶ እንዲፈነጭ አልፈለግኩም ነበር።

የማላውቀው ሰው ጆሮዬን ተጠግቶ እንዲያቃትትብኝ አልፈለግኩም ነበር። ግን ሰውየው አስገድዶ አላመጣኝም። አልደፈረኝም።

ያስገደደኝ ኑሮ ነው።

የደፈረኝ ድህነት ነው።

ሲነጋና ከኔ ጋር ያለውን ጣጣውን ሲጨርስ፣ የሰጠኝን አምስት መቶ አዳዳስ ብሮች እንደያዝኩ በትእዛዝ ያወለኩትን ልብሴን በከፍተኛ ፍጥነት ለበስኩ። ያወለኩት ክብሬ ግን አልጋው ላይ ቀርቷል።

"ቅዳሜ እመጣለሁ....ማን ብዬ ላስጠራሽ ?" አለኝ በተኛበት።

እንድሄድ ፈልጓል። አገልግሎቴ አብቅቷል። አሁን እንደተፋቀ የሞባይል ካርድ ነኝ። አሁን እንደተጫረ የክብሪት ዕንጨት ነኝ። በድጋሚ በጉጉት የሚያየኝ በሚቀጥለው ቅዳሜ መጥቼ እፎይ ማለት ሲያምረው ነው። ስሜን ነግሬው ዞር አልኩና ቦርሳዬን አንጠልጥዬ ለመሄድ ስዞር፣

"ማነሽ...እ...በሩን በደንብ ዝጊው!" አለኝ፣ አልጋው ላይ ተገላብጦ ጀርባውን እየሰጠኝ። ፊት እንኳን የማይገባኝ ሰው መሆኔን ሲነግረኝ ነው በጀርባው የሚያናግረኝ፣ የሚታወስ ሰም እንደሌለኝ ሲነግረኝ ነው ማነሽ ያለኝ።

ይሄን ሳስብ ተዛባሁ፣ ተዛነፍኩ።

ካለ አጥንት እንደተፈጠረ ሰው ሰውነቴ ለመቆምም ለመሄድም እምቢ እያለ ወደ ታክሲ ተራው ሄድኩ። ተኝቶ የነጋለት ሰው ይተራመሳል።

ታክሲው ውስጥ ገብቼ መስኮቱን ደገፍ አልኩና ያለ እቅድ ስቅስቅ ብዬ ማልቀስ ጀመርኩ። ከዐይኔ ግድብ የሚፈሰው እንባ ጉንጬቼ ላይ የሚያደርቅ ሳይሆን አዋሽ ወንዝ ለመግባት ያልም ይመስል ይንዠቀዠቃል።

ከክብሬ ጋር አውልቄው የነበረው የአንገት ልብሴ ላይ ያርፋል።

ከክብሬ ጋር አውልቄው የነበረው ጃኬቴ ላይ ያርፋል።

ከክብሬ ጋር አውልቄው የነበረው ሱሬዬ ላይ ያርፋል።

በለቅሶዬ መሃል፣ "አይዞሽ... ሁሉም ያልፋል" የሚል ድምፅ ሰማሁና ዞርኩ። ከእኔ በእድሜ የምታንስ ልጅ ናት።

"ሁሉም ያልፋል" የሚል የታክሲ ጥቅስ አንብባ የምትደለለው ለዚያ ነው። ትንሽ ልጅ ስለሆነች፣ በቂ ስላልኖረች። አንዳንድ ነገሮች እንደኔ ላለው ሰው እንደማያልፍ የሚያስተምራት የህይወት ልምድ ስለሌላት፣ ቀልደኛ!

ዝም ብዬ አየሇትና በእሽታ ጭንቅላቴን ነቅንቄ ተመልሼ ወደ መስኮቱ ዞርኩ። ሁሉም ቢያልፍ ኖሮ ዛሬ እዚህ ታክሲ ውስጥ እያለቀስኩ ባልተቀመጥኩ፣ ሁሉም ቢያልፍ ኖሮ ለአምስት መቶ ብር አምስት መቶ ቦታ ባልተሰባበርኩ። ሁሉም ቢያልፍ ኖሮ እኔ ትርሲት የአቶ ከለላውና የወይዘሮ ሥምረት ሴት ልጅ፣ የብሌን ታላቅ እህት፣ የዳዊት ታናሽ እህት፣ የዳግም ፍቅረኛ ሀኜ በቀረሁ። አሁን ግን ትርሲት ሸለዋ ነኝ።

ሸሌ ነኝ፣ ሸሌ ብቻ።

ይህንን ሰውየው ዐይን ውስጥ ዐይቼዋለሁ። ይሄንን ሰውየው ትእዛዝ ውስጥ ሰምቼዋለሁ። ይህንን ሰውየው፣ "በሩን በደንብ ዝጊው" ንግግር ውስጥ አድምጭዋለሁ።

ሸሌ ነኝ።

ለማንበብ ደቂቃ የሚፈጅ ሥም በመስጠት የ'ኔን ሥራ ቅዱስ ማድረግ አይቻልምና፣ የለም፣ አንቺ እኮ 'በወሲብ ንግድ የተሰማራች ሴት' ነሽ!" ብላችሁ አታፅናኑኝ።

ከዛሬ ጀምሮ ሸሌ ነኝ።

በረሀብ እያዛጋሁ ቤቴ ገባሁና ከሰል አቀጣጠልኩ። ሳልበላ ውሃ ላፈላ። ሳልበላ በፈላ ውሃ ልታጠብ። ሳልበላ በፈላ ውሃ ገላዬን ልታጠብ። ሸሌነቴን በፈላ ውሃ ሙልጭ አድርጌ ልታጠብ።

ውሃው እስኪፈላ፣ ልብሶቼን አውልቄ ከሌሎቹ ልብሶቼ ጋር እንዳይቀላቀሉ በቤቴ አንዷ መአዘን ላይ ሰብስቤ ጣልኳቸው። ብዙ ልብስ የለኝም፤ ግን እነዚህን ልብሶች መልሼ የምለብሳቸው አይመስለኝም።

'ራቁቴን የሰመጠች አልጋዬ ላይ ቁጭ ብዬ ውሃው እስኪፈላ እየጠበቅኩ ቤቴን ዐየሁት። ለሰው የሚነገር ነገር ስለሌለኝ እንትኑ እዚያ ጋር፣ እትኑ ደግሞ እዛ ጋር አለ ብዬ ላወራችሁ አልፈልግም። በዋጋ ከተሰላ፤ አሁን ያለኝ፣ ዋጋ የከፈልኩበት አምስት መቶ ብር ብቻ ነው። አልጋዬ ላይ የተቀመጠው አምስት መቶ ብር።

ምንአልባት ካልገመታችሁ፣ እንዲህ ያለው ዋጋ ያልከፈልኩበት ብር ለማግኘት ሞክሬ ነበር። ማለቴ ዘልዬ ሸሌ አልሆንኩም። አሳጥሬ ልንገራችሁ። ሁሉንም ሥራ ሰርቻለው። ግን እኔንና እኔን የሚጠብቁ ቤተሰቦቼን ሆድ ፀጥ የሚያደርግ፣ አንገት ቀና የሚያደርግ፣ ደረት አስነፍቶ የሚያስኬድ ሥራ አላገኘሁም።

እውነቴን ነው የምላችሁ፣ እንጀራ ፍለጋ ሴት የሆንኩት ሰው ሆኜ ስላልተሳካልኝ ነው።

ልድገመው፣ እንጀራ ፍለጋ ሴት የሆንኩት ሰው ሆኜ ስላልተሳካልኝ ነው።

የሥጋ ለሥጋን ኑሮ የመረጥኩት ሌላ ነገር ሆኜ መኖር ስላልቻልኩ ነው። ለምሳሌ የሆነ ሰሞን የሆነ "ኤን ጂ ኦ" ሸሌ የመሆን አዝማሚያ ያሳየነውንም፣ ገብተው የተንቧቹበትንም ሴቶች ሰበሰበና፣ "ከዚህ አስነዋሪና ቆሻሻ ሥራ ነፃ እናውጣችሁ፣....ያልገባችሁትንም እናድናችሁ" አለን።

"አልጋ አንጣፊ ስለሆነች ከአልጋ ለመውደቅ ቅርብ ነች" ብለው ነው መሰለኝ፣ ፕሮጀክቱ ውስጥ አስገቡኝ። ደስ ብሎኝ ገባሁ። ኤን ጂ ኦው፣ "አማራጭ የገቢ ማግኛ ዘዴዎች" በሚል ለግማሻችን ጥልፍ፣ ለግማሻችን ዳንቴል ስራ አስተምሮ፤ "በሉ እንግዲህ ሂዱና ንፁህ ስራችሁን እየሰራችሁ በብልፅግና ኑሮ" ብሎ አንድ ኮንቴነር ቤት ተከራይቶልን ሄደ።

እኔ ከጥልፎቹ መሀል ነበርኩ። እንደተማርኩት እየጠለፍኩ አዲሱንና ንፁሑን ሥራዬን ነጻ መውጫዬ፣ መልካም እጣ ፈንታዬ፣ የእግዜር ካሳዬ አድርጌ ተቀብዬው ሥራ ጀምሬ ነበር።

ብዙዎቻችሁ፣ " እንዴ ሸሌ የሆነች ወይ ለመሆን ያኮበኮበች ሴት ሁሌም ሸሌ ናት" ብላችሁ እንደምታስቡ አውቃለሁ። "በሚኒ ስከርት መንገድ መቆም የለመደች ሴት፣ በ'እስከ ጉልበት' የሥራ ቀሚስ ቢሮ መቀመጥ አትችልም ብላችሁ እንደምታምኑ ከውቃለሁ።

የራሳችሁ ጉዳይ
👍31
እኔ ግን በዛ ሰሞን እፎይታ ተሰምቶኝ ነበር።

ሳልጠፋ ስለተገኘሁ ደስ ብሎኝ ነበር።

ሸሌ መሆን የሚያጓጓኝ ሰሞን፣ የከጃጀለኝ ሰሞን አልጋ አንጣፌ ሆኜ የምሰራበት ቡና ቤት ውስጥ ያሉ የሚቀርቡኝ ሸሌዎችን ገድልና እሮሮ በታላቅ ትኩረት፣ በቀን በቀን እሰማ ነበር። ዐይ ነበር።

በመሸ ቁጥር፣ በ'ኮንደም አድርግ አታድርግ" ጭቅጭቅ፣ በጭንቅላቱ ሳይሆን በእንትኑ የሚያስብ ወንድ ጋር እየተጣሉ በፖሊስ መዳኘት አለ፣ በሚሉት የማስፈራራያ ወሬዎች ተሰላችቼ ነበር።

"በጥፊ ካልመታሁሽ ደስ አይለኝም!" እያለ፣ "ከላይም ከታችም ከሚደበድበኝ ወንድ ጋር አድሬ የከፈለኝን ገንዘብ በድብደባ ያበጠ ፊቴን ለመታከም ማዋሉ መረረኝ" በሚሉ ሴቶች ዋይታ ተማርሬ ነበር።

እሺ...ዝርዝሩ ይቅርባችሁ እና እንዲያው በደፈናው፣ በጨለመ ቁጥር ባለተራ ወንድ እላዬ ላይ ስለማይደፋደፍብኝ የእውነት ደስ ብሎኝ ነበር። ከዚህ እጣ ፈንታ ለጥቂት ስላመለጥኩ፣ ደስ ብሎኝ ነበር።

እናም፣ ቀን ቀን እየጋለ አቅልጦ እንደው ውሃ ሊያፈሰኝ በሚዳዳው ሙቀት፣ ሲመሽ ሲመሽ ጥፍር አውጥቶ ሰውነቴን በሚቦጫጭቅ ብርድ ሳልማረር፣ እዛች ኮንቴነር ውስጥ ቁጭ ብዬ ጥልፊን እጠልፍ ነበር።

በየወሩ፤ "አሁንስ በቃኝ...እንኳን ትርፍ ሊያመጣ ለሚያከስር ስራ ደግሞ!" እያሉ ከጥልፉም ከዳንቴሉም ጎራ ወጥተው ሸሌነትን የመረጡ፣ ወይም ወደ ሸሌነት የተመለሱ ጓደኞቼን እያየሁ እንኳን በንፅህና ጎዳና ለመቀጠል ብዙ ለፋሁ።

ብዙ ታተርኩ፣ ብዙ ወጣሁ፣ ብዙ ወረድኩ።

ንጹህ ስራዬ ግን ከሰው በታች አደረገኝ እንጂ ከፍ አላደረገኝም። ሱቄን የሚደጎበኙ ወንዶች ሁሉ፣ ጥልፍ የጠለፍኩበትን አልጋ ልብስ ከመግዛት ይልቅ እኔን ጠልፈው አልጋ ውስጥ ማስገባት ነበር የሚታትሩት። በአምስተኛው ወር የከሸፈውን ፕሮጀክት ተከትሎ የከሸፈውን ህልሜን ኮንቴነሩ ውስጥ ጥዬ ወደ "ሰጥቶ የመቀበል" አለም መጣሁ።

የዛሬው ሰውዬ የመጀመርያዬ ነበር።
"ሀ" ዬ አንደኛ ክፍሌ።

ሳልዋረድ መብላት ብፈልግም፣ ሳልገላመጥ መኖር ብሻም የሞከርኩት ሁሉ አልሳካ ብሎኝ ሸሌ ሆንኩ።ባላያችሁትና ባልኖራችሁት ሕይወቴ ፈርዳችሁብኝ ብትሰድቡና ብትረግሙኝም፣

ዓለም ስትፈጠር ገና ያኔ ከገበሬነት በፊት፣ ከአናጢነት በፊት፣ ከአስተማሪነት በፊት፣ ከምንም አይነት ሥራ በፊት፣ "ሲወርድና ሲዋረድ" እዚህ የደረሰውን ሥራዬ ግን በእርግማንና በስድብ ወጀብ ከምድረ ገፅ እንደማይጠፋ ታውቁታላችሁ

ምክንያቱም፣ በጨለማ ዝቅ ብዬ ያገኘሁት ገንዘብ እጄን የሚጠብቁ ቤተሰቦቼን ከፍ እንደሚያደርግልኝ አውቃለሁ።

ቀን የተጠየፉኝ ሰዎች ማታ እንደሚያመልኩኝ አውቃለሁ።

ቆሻሻው ስራዬ ንጹሕ እንጀራ እንደሚገዛ አውቃለሁ።

ስለዚህ፣ ወንድ ሊሆን የሚመጣን ወንድ ሴት ሆኜ እያስተናገድኩ እንደ ሰው እኖራለሁ። ሸሌ ነኝ።ከዛሬ ጀምሮ ሸሌ ነኝ።

💫አለቀ💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍1
አትሮኖስ pinned «#ሸሌ_ነኝ ፡ ፡ #በሕይወት_እምሻው ፡ "ነይ እዚህ ጋር ! ልብስሽን አውልቀሽ ውስጥ ሳትገቢ...ብርድ ልብሱ ላይ ተኚ" ሲለኝ፣ ልማድ ሆኖብኝ መግደርደር ዳድቶኝ ነበር። ድሮ፤ ልጃገረድ እንዳለሁ ግዜ መሽኮርመም። ሰው እንጂ ሴት ያልሆኑኩ መስሎኝ፣ ሥጋ ሸጬ እንጀራ ልገዛ ያልመጣሁ መስሎኝ። አንገቴን እንደሰበርኩ ወደ አልጋው ሄድኩ ሲያገኘኝ እሄድ እንደነበረው አይደለም አካሄዴ።ሰበር ሰካ የለውም፣…»
#አኩራፊ_ሰው_ብዙ_ነገር_ያመልጠዋል
===
ባል እና ሚስቱ በመሀላቸው ግጭት ተፈጥሮ አይነጋገሩም፡፡ ሁለቱም በረጅም ትዝታ ተውጠዋል፡፡ መጀመሪያ ማውራት ሽንፈት መስሎ ስለታያቸው ሳይነጋገሩ መተኛ ሰዓታቸው ደረሰ፡፡
ድንገት ግን ባል የሆነ ነገር ትዝ አለው፡፡ ነገ በጠዋት የስራ ስብሰባ ለመታደም ወደ ሌላ ሀገር ለመሄድ በረራ አለው፡፡ ሁሌ ደሞ ወደ ስራ ሲሄድ እንቅልፋም በመሆኑ የምትቀሰቅሰው ሚስቱ ናት፡፡ እናም የነገው ስበሰባ እንዳያመልጠው ለሚስቱ "11 ሰዓት ቀስቅሽኝ" ብሎ በአፉ መናገር ሞት መስሎ ታየው፡፡ እና ወረቀት ላይ "ነገ የስራ ስብሰባ ስላለበኝ ወደ ሌላ ሀገር እበራለው፡፡ አደራ 11 ሰዓት ቀስቅሽኝ" ብሎ በወረቀት ፅፎ እሷ የምታየው ቦታ አስቀምጦላት ምንም ቃል ሳይተነፍስ ተኛ፡፡
ጠዋት ሰውየው ከእንቅልፉ ሲነቃ ከጠዋቱ 3ሰዓት ሆኖ በረራውም ስብሰባውም አምልጦታል፡፡ "እንዴት እንደዛ አስጠንቅቄ ነግሪያት አትቀሰቅሰኝም?" ብሎ በጣም ተበሳጨ፡፡ ከአልጋው ለመነሳት ሲሞክር አንድ ወረቀት ኮመዲኖ ላይ ተቀምጦ አየ፡፡ "11 ሰዓት ሆኗል ተነስ ስብሰባ እንዳያመልጥህ" የሚል ፁፍ ተፅፎበታል፡፡
ማነው ስህተት የሰራው? ማነው ልክ?

አስተያየቶን አድርሱን @atronosebot
#ያቺን_ልጅ_ንገሯት

እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያቺን ልጅ ንገሯት
ልከ እንዳገሩ ነዉ የሚወድሽ በሏት
አዎ እንዳገሬ ነዉ…
እንደ ምንጩ ጣእም እንደ አፈሩ ሽታ
ልጎንጭሽ የምላት…
ልዳብስሽ የምላት ጠዋትና ማታ
ለብሻት የምኖር…
እንደ ቀዩ ጃኖ እንደ ነጩ ኩታ
ጋቢዋ ነኝ እኔ…
ጠላት የተኮሰዉ ንፋስ እንዳይነካት
ሁለት ግዜ ዙሬ…
ወገቡዋ ላይ ያደርኩ የማርያም መቀነት
እንደ አገር አርጅታ…
እንደ አገር አዉግታ ደግሞ ተበሳጭታ
እድሜዉ ይሁን ንዴት ጸጉርዋን አሸብታ
አፋፉ ላይ ቁማ…ብቻዋን ቆዝማ
ድንገት ብታገኟት…
እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያቺን ልጅ ንገሯት
ልክ እንዳገሩ ነዉ የሚወድሽ በሏት
ንገሩልኝ ዘመድ ንገሩልኝ ወገን
እኔ በሷ ፍቅር እንዴት እንደምሆን
እንደተዋለበት ጤናዉን እንዳጣ
በጠላ አስተናግር በጥብጦ እንደጠጣ
ያስለፈልፈኛል ጩህ ጩህ ያሰኘኛል
የቀኑ ሳይበቃዉ ሌሊት ያስዞረኛል
ጎርፉን እጠጣለሁ አፈር እቅማለሁ
ጎርፉን እየጠጣሁ….ሃገሬን እላለሁ
ጨለጥኳት እላለሁ
አፈሩን እየቃምኩ….ሃገሬን እላለሁ
በላሁዋት እላለሁ
ጸጉሬን እነጫለሁ ልብሴን እቀዳለሁ
እንዳይሆን እንዳይሆን እንዳይሆን ሁኛለሁ
እናም ያች የኔ…
የምጠብቃት ሴት የመጣች እንደሆን
መስከረምን አልፋ…
ጥቅምትን ተሸግራ ህዳሩ ሲታጠን
ገላየ ቆሽሾ አካላቴ ዝሎ
ገጼ ተጎሳቅሎ
ድንገት አልፋኝ ብትሄድ…
ፍቅሬ ተዘንግትዋት…
ማንነቴ ጠፍትዋት…
እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያቺን ልጅ ንገሯት
እንዳገሩ ነበር የሚወድሽ በሏት።

🔘በሰለሞን ሳህለ🔘
አትሮኖስ pinned «#ያቺን_ልጅ_ንገሯት እኔ ቃል ጨረስኩኝ ያቺን ልጅ ንገሯት ልከ እንዳገሩ ነዉ የሚወድሽ በሏት አዎ እንዳገሬ ነዉ… እንደ ምንጩ ጣእም እንደ አፈሩ ሽታ ልጎንጭሽ የምላት… ልዳብስሽ የምላት ጠዋትና ማታ ለብሻት የምኖር… እንደ ቀዩ ጃኖ እንደ ነጩ ኩታ ጋቢዋ ነኝ እኔ… ጠላት የተኮሰዉ ንፋስ እንዳይነካት ሁለት ግዜ ዙሬ… ወገቡዋ ላይ ያደርኩ የማርያም መቀነት እንደ አገር አርጅታ… እንደ አገር አዉግታ ደግሞ…»