አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
572 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
​​በዚህ ጊዜ የሆነ የቆርቆሮ በር ያለው ግቢ ደርሰው ነበር..ስንዱ እጇን  አሻግራ ከውስጥ የተሸነጎረበትን እንጨት ሳበችና በራፉን ከፈተች.. ተያይዘው ወደውስጥ ሲገቡ አንድ ጠና ያሉ ሴት ከበረንዳ ላይ ተቀበሏቸው
‹‹እንዴት ዋልሽ ልጄ..?ደህና ዋልሽ….?››ለሁለቱም የሞቀ ሰላምታ ሰጣቸው፡፡‹‹ግቡ  ግቡ …››ወደውስጥ ዘልቀው ሲገቡ ሶስት ክፍል ያለው ያረጀ ቤት ነው ፡፡ሰፋ ያለው ሳሎን መሰል ክፍል ውስጥ ሶስት አልጋ ተዘርግቷል፡
አንዱ አልጋ ባዶ ሲሆን ሁለቱ አልጋ ላይ አንድ አንድ ሰው ቁጭ ብለዋል፡፡አንዱ አልጋው ጠርዝ ላይ  ተቀምጧል  ፡፡ሙሉ  ፀጉረ  በረሀ  ነው…እድሜው  ከሀምሳ ትንሽ ከፍ ይላል፡፡አንድ እግሩ መሬት ረግጧል… ሌለኛው እግሩ ግን ግማሽ ነው.. በፋሻ ተጠቀልሎ ክራንች ላይ ተንጠልጥሏል፡ቀጣዩ አልጋ ላይ ያለውን ስታይ ጭራሽ ሁለቱ እግሮቹ ከጉልበቱ በታች ተጎምደዋል..ልክ እንደአባቷ..በተጨማሪም የግራ እጁ እጣት አልባ ነው፡፡
ስንዱ ሁለቱንም በስማቸው እየጠራች ስለጤናቸው ትጠይቃቸዋለች፡፡
‹‹አንቺ  እያለሽልን   ምን   እንሆናልን…?እግዚያብሄር   ከክፉ   ሁሉ   ይጠብቅሽ፣..ከእነቤተሰብሽ ክፉ አያግኝሽ..› በየተራ እየተፈራረቁ ይመርቋታል….ሳባ ባለችበት ደንዝዛ ቆማለች፡፡
ተዋወቋት ሳባ እያልኩ የማወራችሁ ልጄ እሷ ነች ››ሁለቱም በየተራ ለሰላምታ እጃቸውን ዘረጉላት፡፡ በደመነፍስ ጨበጠቻቸው፡፡ይዛት ወደሚቀጥለው ክፍል ስትገባ ሌሎች የተለያየ ጉዳት የተጎዱ ሁለት ሴቶች አሉ፡፡ በአጠቃላይ እዛ ቤት ውስጥ  እራሳቸውን  ሙሉ  በሙሉ  መርዳት  የማይችሉ  ከጉዳታቸው  ያላገገሙና  በህክምና እርዳታ ላይ የሚገኙ ሰባት ሰዎች ነበሩ…፡፡
ከ30 ደቂቃ ቆይታ በኃላ ምንም ሳይነጋገሩ በዝምታ እንደተሸበብ ወደ ቤት ተመለሱ፡፡
..ሳሎን  ባለ  ሶፋ  ላይ  ጎን  ለጎን  እንደተቀመጡ  ነው  ሰባ  ንግግሩን  በጥያቄ  የከፈተችው፡፡
‹‹ስንድ አልገባኝም…ምንድነው ያሳየሺኝ?››
‹‹ካየሻቸው ጉዳተኞች መካከል ሶስቱ በአሁኑ ጦርነት የተጎዱና ጡረታ ወጥተው ወደቤተሰባቸው የተመለሱ ቢሆን በጣም ዝቅተኛ በሆነ ቤተሰብ ውስጥ ያሉ በመሆናቸው በከፋ ሁኔታ ስቃይ ላይ ሆነው ስላየኋቸው ነው አሁን ወዳሉበት ቦታ ያመጣዋቸው ፡፡ሌሎቹም ሁለቱ በመኪና አደጋ  የተጎዱ  ሲሆን  የተቀሩት በተለያየ መንገድ አካላቸውን አጥተው አሁን ህክምና ክትትል ላይ የሚገኙ ናቸው፡፡ይሄንን ቤት ተከራይቼ ያየሻትን አስታማሚና ተንከባካቢ ቀጥሬላቸው በተቻለኝ አቅም ላሳክማቸውና የኑሮ ሸክማቸውን ለቃልልላቸው እየሞከርኩ ነው፡፡››
‹‹ይሄ ሁሉ ከመቼ ጀምሮ ነው?››
‹‹አመት ሊሆነኝ ነወ….እርግጥ ሰባቱንም በአንዴ አይደለም የተቀበልኳቸው.. በተለያየ ጊዜ ነው፡፡ ድነውና የተሻለ አማራጭ አግኘተው የሄዱም  ሁለት  ሌሎች ነበሩ..››
እንባ ያቀረዘዙ አይኖቾን በናብኪን እያበሰች፡፡‹‹ስንድ በጣም የሚገርም ስራ ነው››አለቻት፡፡
‹‹ሳቢ ይሄንን ለምን እንደማደርግ ታውቂያለሽ?››ስትል ስንዱ ጠየቀች፡፡
‹‹አዎ አውቃለሁ....የአባቴን መንፈስ ደስ ለማሰኘት ነው..እሱ በምድር ላይ የመጨረሻዎቹን የጉዳትና የህመም አመታትን ባሳለፈው አይነት ስቃይ ውስጥ
እያሳለፉ ያሉትን ሰዎች በመርዳት ነፍሱን ማሳረፍና ማስደሰት ስለፈለግሽ ነው፡፡››በእርግጠኝነት መለሰች፡፡
‹‹አይደለም..ለእሱ ብዬ አይደለም››
ሳባ ያልጠበቀችውን መልስ ስላገኘች ደነገጠች‹‹እና ታዲያ ለምንድነው?›
‹‹ለአባትሽ ራሱ በህይወት ሳለ በተቻለኝ መጠን ተንከባክቤው አስታምሜውና ብቸኝነት እንዳይሰማው አድርጌ ስለሸኘሁት ይሄንን ባደረኩለት ኖሮ ብዬ የሚቆጨኝ ነገር የለም…ይሄንን እያደረኩ ያለሁት ለአንቺ ብዬ ነው››
ሳባ አስፈሪ ድንጋጤ ደነገጠች‹‹አልገባኝም ለእኔ እንዴት?›
‹‹አንቺ አባትሽን ካጣሽ በኃላ ምን አይነት ስቃይ ላይ እንዳለሽ አውቃለሁ…ፈፅሞ መቀበል አልቻልሽም ...በመጀመሪያ አባትሽን ያሳጣሽ ድህነት መስሎሽ ቀንና ሌት በመስራትና የማትፈልጊያቸውን ነገሮች ሁሉ በማድረገ ገንዘብን ሰበሰብሽ … ሀብታም ሆንሽ… ግን ሀዘንሽን ሊያረግብልሽ አልቻለም…አሁን አሁን  ደግሞ  የአባትሽ  ሞት ሰበብ ራስሽ እንደሆንሽ በማሰብ ነፍስሽን እየተጠየፍሽ ራስሽንም እየቅጣሽ ነው፡፡በዚህ መንገድ ከቀጠልሽ እመኚኝ አንቺም ብዙ እድሜ የለሽም..እና ከአባትሽ መንፈስ የተጣላሽና የተቀያየምሽ ምስሎ ይሰማሻል››
‹‹ስንድ ልፊ ቢልሽ እኮ ነው …ያማ ምን ሚያጠራጥር ነገር አለው?››
‹‹እሱ ላይ ልከራከርሽ አልፈልግም..አንቺ በራስሽ በምታውቂም ምክንያት አባትሽ ቅር እንደተሰኘብሽ ወስነሽ ቢሆን እንኳን ከእሱ መታረቂያ መንገዱ አሁን አንቺ እየተጓዝሸበት ያለው የጥፋትና የውድመት መንገድ አይደለም…ይሄ አሁን እኔ ያሳየሁሽ መንገድ ነው ትክክለኛው፡፡የአዲስአባ ህይወት ይብቃሽ…እየዋጠሸና እያሰመጠሸ ነው….እኔና ልጄ በጣም ነው የምንወድሽ…ለእኛ  ስስታችን ነሽ…ከአባትሽ ሀዘን የተፅናናንብሽ የህይወት  ተስፋችን  ነሽ፤እባክሽ  እዚህ  ነይ አብረን አንኑር..እነዚህን ሰዎች ተንከባከቢያቸው.. ልክ እንደአባትሽ እያየሽ እርጂያቸው ፤እኔም ከጎንሽ ነኝ…እዳ ምናምን ካለብሽ እዛ  ያለውን  ቤትሽን ሽጭውና ከፋፍለሽ ነፃ ሆነሽ ባዶ እጅሽን ነፍስሽን ብቻ ይዘሽ ነይ..እዚህ ለሁለችንም የሚበቃ ነገር አለ …እኔ እናታችሁ መቼም አንገታችሁን እንድትደፉ አላደርግም..፡፡››
‹‹ስንድ ቆይ ግን እቤቱን ለምን ተከራየሽ…ፍቅር ቤቱን አላከራየሽውም ወይ  አልኖረሽበት..?
‹‹አስቤ ነበር.. ግን ይህ ቤት የአንቺና የወንድምሽ  ንብረት  ነው...ፍቃዳችሁን ሳልጠይቅ እናንተን ቅር የሚየሰኝ ነገር ማድረግ አልፈልግም..፡፡››
‹‹አይ ስንድ .ይሄ ቤት የእኛ ሳይሆን የአንቺ ነው...እናም ምንም ነገር ለማድረግ የእኛ ፍቃድ አያስፈልግሽም››
‹‹..እኔ ለአባቴ አልገባውም፡፡››
‹‹ለምን  አንዲህ አይነት ጨለማ ሀሳብ ከአእምሮሽ ማስወጣት እንዳቃተሸ ታውቂያለሽ ? የህመምሽ ዋና መንስኤ ይሄ መጥፎ ሀሳቦችን ወደራስሽ የመሰብሰብ አባዜ ስለተፀናወተሸ እንደሆነ ታውቂያለሽ››
‹‹እኔ እሱን አውቃለሁ…አንቺ ግን አባቴን እንደገደልኩት አታውቂም››
‹‹አባትሽን የወሰደው ፈጣሪ ነው ማንም አልገደለውም….እስትንፋሱ ስትወጣ እንኳን   አንቺን እየመረቀና እያመሰገነ ነበር የሞተው፡፡››
‹‹ለምን  እንዳዛ  እንዳደረገ  ታውቂያለሽ.?.በስተመጨረሻ  ልጁ  የማትረባ  ውዳቂ መሆኗን ስላወቀ እፍረት ተስመቶት ነው፡፡››
‹‹ስለምንድነው የምታወሪው?››
‹‹ለማንኝውም እርሺው…››አለችና…ከተቀመጠችበት ተነሳችና ወደመኝታ ቤት በመሄድ ይዛ የመጣችው ቦርሳ አንጠልጥላ ወደ ሳሎን ተመለሰች…ከቦርሳ ውስጥ  ቼክ አወጣችና አምሰት መቶ ሺ ብር ፃፈችበት፡፡
ስንድ እንደአንቺ አይነት እናት እና ጓደኛ ስላለኝ በጣም እድለኛ ነኝ...እኔ የማረባና ከንቱ ሰው ስለሆንኩ አይገባኝም እንጂ አንቺና ወንድሜ ለእኔ ያላቸሁን ፍቅር ብቻ ቢሊዬን ብር አይገዛውም..አሁን ልሂድ አንድ ሁለት  ወር  ላስብበት..ከዛ ተመልሼ እመጠና እናወራበታለን.እስከዛ ይህቺን ያዣት፡፡››
‹‹እኔ እኮ ብር አልጠየቅኩሽም.ብርም አልተቸገርኩም››
‹‹አውቃለሁ..ካለሽ አስቅምጪው…ሲቸግረኝ መልሼ ወስዳለሁ›› አለቻት ፡፡›››
‹‹‹ ፣እሺ ካልሽ ብላ መኪናዋ ድረስ ሸኘቻት፡፡

💫ይቀጥላል💫

ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube 

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍8815👏3😱1
አትሮኖስ pinned «#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ ፡ ፡ #ክፍል_አስራ_ስድስት ፡ ፡ #በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ ዛሬ ላይ ሳባ  ሊቱን  ሙሉ  በትዝታ  ከወዲህ  ወዲያ  ስትዋዥቅ  ነው  ያደረችው…ለሰከንድ እንኳን እንቅልፍ በአይኗ አልዞረም…አሁን የትዝታ ጉዞዋን መሀከል ላይ ሳትቆጭ ያቆመችው ታናሽ ወንድሟ ራጂ የተኛችበት ክፍል ደረስ መጥቶ በእናቱና በእሷ መካከል ሰርስሮ መሀከላቸው ሲገባ ነው፡፡ ‹‹አንተ ጓረምሳ ሴቶች ክፍል ምን…»
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ


#ክፍል_አስራ_ሰባት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ሳባ የአሰላን ከተማ ለቃ እንደወጣች በደመነፍስ ነበር ስትነዳ የነበረው፡፡ ሀሳቧ ሁሉ ወደኃላ ተመልሷል..ያንን የተረገመ ስራ እንዴት እንደ ጀመረች አስር  አመት ወደኃላ ተመልሳ ማብላላት ጀመረች፡፡
ከ10 ዓመት በፊት
ያኔ በዛ ዘመን አዲሱን ስራዋን ለመጀመር ከሰገን  ጋር የመጨረሻ ድርድር ስታደርግ እና ሲለያዩ አንድ ምክር ሰጥታት ነበር…‹‹ድንግል ከሆንሽ ለምትወጂው ሰው ስጪው፡፡››ነበር ያለቻት…ግን በፍጥነት ማድረግ አልቻለችም ነበር…በወቅቱ የምትወደው ሰው ልቧን ሰብሮ ካሳዘናት ሰነባብቷል….‹‹ለእሱ ድንግልና ሳይሆን ከተቻለ በቀል ነው የሚገባው››ስትል  በማሰብ….ስለድንግልናዋ ማሰብና መጨነቅ ትታ…ዕቃዋን በየካርቶኑ እያስገበባች አሸገች፤ልብሶቿን በሁለት ሻንጣ ጠቅጥቃ አሳሰረች…የምትተኛበት ፍራሽ ብቻ እንደተዘረጋ ቀረ…ቀጥሎ ምን እንደምታደርግ ግራ ገባት፡፡መቼስ ይሄን ሁሉ ኮተት ይዛ በህዝብ ትራንስፖርት ተጠቅማ አሰላ ድረስ ማጓጓዝ አትችልም...እንዴት አድርጋ…‹‹ደግሞ ስኖርበት ባዶ የነበረው ቤት  አሁን ልለቅ ስል እንዴት ነው እንዲህ ሜዳውን የሞላው?››ሥትል በማሰብ ተገረመች፡፡‹‹ግን አሁን ይሄንን ሁሉ ኮተት ብረት ድስት፤ሰሀን፤ብርጭቆ ምድጃ ለምንድነው የሰበሰብኩት? ለምን ለተቸገረ አላከፋፍለውም?››ራሷን በትዝብት ጠየቀች፡፡
  ግን ደፍራ ነገ ሀብታምና  ሁሉ  ነገር  የተረፈው  እንደምትሆን  ተማምና ‹‹አይ ይሄን ኮልኮሌ አልፈልግም ላከፋፍለው››ልትል አልቻለችም…
ወሰነች.‹‹አዎ ብር አለኝ… አሰላ ድረስ የሚወስድልኝ መኪና ብፈልግ ይሻላል››ስትል አሰበች…‹‹አዎ መርካቶ ብሄድ ጭነት መኪና አላጣም….ጭነው ሲጨርሱ በዚሁ ጎራ ቢሉ ከላይ ጣል ጣል አድርገው ይወስዱልኛል….››ብላ ስሌት ሰራችና ወደመርካቶ ለመሄድ ካሰበች በኃላ ሌላ የተሻለ ያለችው ሀሳብ ብልጭ አለላት፡
ደምሳሽ ትዝ ኣላት….እርግጥ በወቅቱ ለዚህ የሚያበቃ ትውውቅም ሆነ ንግግር.አልነበራቸውም...ቢሆንም.ያው‹‹ቤተሰብ ሆነናል››ብሏት የለ. ብትጠይቀው ምንም ክፋት እንደሌለው አሰላች…ሸፌር ስለሆነ ሌሎች ሹፌሮችን ስለሚያውቅ ወደአሰላ የሚሄድ የጭነት መኪና ብዙም ሳይለፋ በስልክ ሊጨርስላት ይችላል…ስልኳን አወጣችና ደወለችለት..ከሶስት ጥሪ በኋላ ተነሳ..
‹‹ጤና ይስጥልኝ የእኔ እመቤት››

‹‹አቶ ደምሳሽ ሳባ ነኝ .አወቅከኝ?በቀደም…››

‹‹እመቤቴ አውቄሻለሁ..ማብራራት አይጠበቅብሽም…አንቺን እንዴት ልዘነጋ እችላለሁ፡፡ለዛውም ቤተሰብ ሆነን?››ነበር ያላት…
‹‹በእውነት ጥሩ ስሜት እንዲሰማኝ ነው ያደረከው››አለችው ከምሯ፡፡
‹‹አረ ምንም የተለየ ነገር አልተናገርኩም…ለማንኛውም ምን ልታዘዝ?››

‹‹እየፈራሁ  ነው  የደወልኩት..ሌላ  ላስቸግረው  የምችል  ሰው  ስለሌለ  ነው እባክህ ከድፍረት አትቁጠርብኝ››

‹‹በነገራችን ላይ  አልተነገረሽም መሰለኝ?››

‹‹ምኑን?››

‹‹ከዛሬ ጀምሬ በማንኛውም ነገር አንቺን እንድጠብቅ፤እንድታዘዝና የምትፈልጊውን ነገር ሁሉ እንዳሟላልሽ ታዝዣለሁ…ስለዚህ እኔን  ማዘዙን ከዛሬው ተለማመጂው…ለአንቺ መታዘዝ ስራዬ ነው›› አላት፡፡
‹‹ማዘዙን?››

‹‹አዎ ማዘዙን››

‹‹አይ እንዳልጠየቅህ አደረከኝ…በቃ ይቅርብኝ ሌላ አማራጭ እፈልጋለሁ፡፡››

‹‹አረ ተይ ቀለል አድርጊውና የምትፈልጊውን ንገሪኝ..ካለበለዚያ አሁኑኑ ሰፈርሸ እመጣለሁ››አላት
‹‹ኸረ ተው…እሺ ያው ሹፌር  ስለሆንክ ሹፌሮችን ታውቃለህ ብዬ ነው››

‹‹አዎ በደንብ አውቃለሁ…ምን ፈለግሽ?››

‹‹የፈለኩትማ ያው ሰሞኑን ስልጠና ጠቅልዬ ስለምገባ የምኖርበትን ቤት ለቅቄያለሁ….ቤተሰቦቼ ያሉት አሰላ ነው…እቃዎቼን ወደእዛ ለመውሰድ  ፈልጌ ነበር…እና ወደዛ የሚሄድ የጭነት መኪና ፈልጌ ነበር..እንዴት እንደማገኝ  ግራ ገብቶኝ ነው››
‹‹ወይ ለዚህች ነው እንዴ..?ለመቼ ነው..?››

‹‹ከተቻለማ ለዛሬ ነው…ካልሆነም ለነገ ጠዋት…››

‹‹ስልኬን ጠብቂ…መልሼ እደውላለሁ፡፡››

‹‹በእውነት ከልቤ ነው የማመሰግነው››

‹‹በይ ቻው በቤተሰቦች መካከል መመሰጋገን የለም ››ብሎ ስልኩን ዘጋ፡፡

ከ8  ደቂቃ  በኃላ  ነበር  ስልኳ  መልሶ  የጠራው…ስታየው  ደምሳሽ  ነው..በዚህ ፍጥነት አልጠበቀችም.
አነሳችውና ‹‹ሄሎ አገኘህልኝ?››አለችው፡፡

አዎ እቃሽ ብዙ ነው እንዴ ?ማለት ፒካፕ መኪና አይችለውም..?››

‹‹አረ በደንብ ነው ሚችለው››

‹‹እንግዲያው አሁን 5 ሰዓት ሆኗል 7 ሰዓት ሰፈር ደርሶ ይደውልልሻል..እስከዛ የቀረሽ ነገር ካለ  አስተካክይ››
በደስታ ስልኩን ዘጋችና የመጨረሻውን ዝግጅት ማድረግ ጀመረች፡


ለ7 ሩብ ጉዳይ ደወለላት...ፈጥና አነሳችው

‹‹ሄሎ ደምሳሽ...እንዴት ሆነልህ?››

‹‹ያው ግሎባል ጋር ሰማያዊ ደብል ፒካኘ ቲዬታ መኪና ይዞ እየጠበቀሽ ነው።››ስልኳን እያወራች ቤቱን ለቃ ወጣች‹‹እንዴት እንደማመሰግንህ አላውቅም"
"ችግር የለውም… ስትመጪ ምሳ ትጋብዢኛለሽ"
‹‹አረ  ችግር  የለውም...ግን  ክፍያውን  እንዴት  ነው  የማደርገው  ማለቴ
ነግሮሀል?"

‹‹ዋጋው ችግር የለውም...ወላጆችሽ ምሳና ቡና ከጋበዙት ይበቃዋል››
‹‹እውነቴን እኮ ነው...ትቀልድብኛለህ አይደል?››
በዚህ ጊዜ ግሎባል ጋር ደርሳ ነበር ...በምልክት የነገራትን ፒካፕ ወዲያው አየቻት...ለሹፌሩ ወደእሷ እንዲመጣ በእጇ ምልክት ጠራችውና መኪናዋን ማንቀሳቀሱን ካየች በኃላ ፊቷን አዙራ ወደቤቷ ተንቀሳቀሰች፡፡
‹‹ሰውዬውን አግኝቼዋለሁ" ‹‹እ..ታዲያ አናገርሽው?"  ‹‹አይ አላናገርኩትም"
"ታዲያ ልደውልለትና ልጠይቅልሽ ወይስ አንቺው እዛው ትከራከሪዋለሽ?"
‹‹አይ አመሰግንሀለሁ...ከዚህ በላይማ ላስቸግርህ አልፈልግም...በቃ ቻው።››
‹‹ቻው በቃ ሚቸግርሽ ነገር ካለ ደውይ››
እሷ የቤቷ በራፍ ጋር ስትደርስ ፒካፗ አጠገቧ  ደርሳ  በስሱ  ክላክስ  ሲያደርግላት ስልኩን ፈጠን ብላ ዘጋችና ወደግቢ ገብታ የመኪና መግቢያ በራፍ ከፈተች… መኪናዋ ወደውስጥ ዘልቃ ገባችና የግቢው መሀል አካባቢ ቆማ ከገቢናዋ  ሹፌሩ ዱብ ብሎ ወረደ...በድንጋጤ እጇን አፏ ላይ ከደነች።
‹‹ምነው አስደነገጥኩሽ እንዴ?››
"እዚህ ሆነህ ነው እንዴ የምታስለፈልፈኝ...?ባለመኪናው የት አለ?"
‹‹መኪናው የድርጅቱ ነው...ሹፌሩም ደግሞ እኔ ነኝ.."
‹‹ኸረ  ደምሳሽ  እንዲህ እኮ   መቸገር  አልነበረብህም።አሰላ  ድረስ  እኮ  ነው።

"ይሄ የእኔ ሀሳብ አይደለም..ታዝዤ ነው...መኪና እየፈለግሽ እንደሆነ ለሠገን ስነግራት...ራስህ አድርስላት ብላ አዘዘቺኝ...ይልቅ አሁን ሰዓቱ እየነጎደ ስለሆነ እቃሺን ቶሎ ጫን ጫን አድርገን እንውጣ›› አላት። እየከበዳት እቃዋን ወደ ተቆለለበት ክፍል ይዛው ገባች..እቃውን ጭነው ከግቢው ለመውጣት 20 ደቂቃ ብቻ ነበር የወሰደባቸው።
///
11 ሰዓት ላይ ቤት ደረሱ እቃው እስኪወርድ፤ መክሰስ በልተው የተፈላውን ቡና ጠጥተው እስኪያጠናቅቁ ለአንድ ሰአት ሩብ ጉዳይ ሆነ...ሳባ    ከቤተሰቦቿ ጋር ስትጫወት አድራ በማግስቱ ረፈድፈድ ሲል ነበር መመለስ   የፈለገችው። ያንን ዕቅድ ያወጣችው ሹፌሩ ደምሳሽ መሆኑን ከማወቋ በፊት ነበር። በኋላ ግን ለእሷ ብሎ አሰላ ድረስ መጥቶ እንዴት ብቻውን እንዲመለስ ትተወው?ያ ነው የጨነቃት፡፡ እርግጥ እርሱም በእንግድነት እነሱ ቤት እንዲያድርና ጥዋት አብረው እንዲመለሡ ጠይቃው ነበር። እሱ በማግስቱ 12 ሰዓት አዲስ አበባ ላይ የሚሰራው ስራ ስላለ እንደማይችል ስለነገራት አብራው ለመመለስ ወሰነች። ሁሉን
👍6810🔥1
ነገር ካጠናቀቁ በኃላ ስንዱን ወደ ውስጠኛው ክፍል ይዛት ገባችና ከቦርሳዋ ውስጥ የታሰረ አስር ሺ ብር በማውጣት እጇ ላይ አስቀመጠች።
‹‹ይሄ ምንድነው?››
‹‹ለቤት የጎደለ ነገር ካለ አሟይበት››
‹‹እንዴ ኧረ እግዜር ይመስገን ምንም የጎደለ ነገር የለም"
"ይገባኛል..ያው እንደነገርኩሽ ለሶስት ወር ስልጠና ልገባ ስለሆነ ጥሩ ብር ነው የተከፈለኝ….እዛ ደግሞ ምግብም ሆነ መኝታ ድርጅቱ ስለሚችለኝ ብዙ ወጪ የለብኝም...እና በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ወግ ይድረሰኝ።እሁድ ፋሲካ አይደል እስኪ እስፓንሰር ልሁን…ፍቀጂልኝ።"
"ውይ ጉረኛ...እንደዛ ካልሽ ለአባትሽ ስጪው"
"እንዴ እያወቅሽ...እሱን በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ለማሳመን መሽቶ ይነጋል"
‹‹አይሆንም አልኩሽ አይሆንም.››
‹‹በይ አሁን ልሄድ  ሰውዬው ይሰለቻል...ጥሩ እናት ሁኚ››
"ሰውዬው ነው ያልሽው?"
"አዎ ምነው.?."
‹‹አይ እንደው ሳየው…ወንዳወንድ ቢጤ ነው"
"እና ምን ለማለት ነው...? አንድ እናት ልጇን በእንዲህ አይነት የብልግና ወሬ በመናገር ማሸማቀቅ አግባብ ነው?"ብላት ጉንጯን ሳመችና ወደሳሎን ተመለሠች።
   ቅዳሜ ተመልሳ እንደምትመጣ ተናግራ አባቷን ተሠናበተችና እንግዳዋን አስከትላ ወጣች፡፡ ግቢው ውስጥ ያቆሟትን መኪና አስነስተው ወደአዲስ አበባ የመልስ ጉዞ ጀመሩ።
ከከተማ እንደወጡ ‹‹ሀገርሽ ታምራለች?››ነበር ያላት፡
"ምን የችኮላ ጉዞ ሆነ”....ዞር ዞር አድርጌ ባስጎበኝህ ደስ ይለኝ ነበር"
"ያው ደጋግመን መምጣታችን ይቀራል።"
"አዎ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ አዲስአበባ ስንት ሰዓት የምንደርስ ይመስልሀል?"
"ሶስት ሰዓት አካባቢ...ምነው ችግር አለው?"
"አይ ያው እንደምታውቀው ቤቴን ለቅቄያለሁ፤ የማድረው 22 አካባቢ የምትኖር ጓደኛዬ ጋር ነው...ኪራይ ቤት ስለምትኖር ሰዓት ካለፈ በኃላ እንዳልደርስ ፈርቼ ነው።
ፈገግ አለ

"ምነው ንግግሬ ያስቃል እንዴ?››አለችው ደንገጥ ብላ፡፡
"በጣም  እንጂ...መቼስ  አብሮ  ያደገ  ማንነትንና  አስተሳሰብን  በአንዴ  ከአዕምሮ መንቅሮ ማውጣት ይከብዳል?
‹‹እንዴት ማለት?አልገባኝም"
"እንዳልገባሽማ አወቅኩ...ቅድም ስንመጣ ከዛሬ ጀምሮ ሳባ ማለት እንዲህ ነች እንዲያ ነች..እያልኩ ለሁለት ሰዓት ላስረዳሽ ሞክሬ ነበር፡፡
‹‹ምኑን?››
"አሁን  እኮ  አንቺ  የዛሬ  ሳምንት  የነበርሽው  ሳባ  አይደለሽም..አሁን  የምታድሪበት ቤት ፈልጋ ጓደኞቿ ቤት የምትንከራተት  ምስኪን አይደለሽም።››
‹‹ለነገሩ እውነትህን ነው..ቤርጎ ይዤ ማደር እችላለሁ...ግን ብቻዬን ሆቴል ይዤ አድሬ አላውቅም፤ ለዛ ነው በፍጥነት ወደምናቤ ያልመጣልኝ።›
‹‹ጥሩ…ለማንኛውም ማድረግ ያለብሽ..ደምሳሽ እኔ የማድርበት ቤት እፈልጋለሁ… ብሎ መናገር ብቻ ነው።ሌላው የእኔ ስራ ነው።››

"እሺ አቶ ደምሳሽ ለዛሬ የማድርበት ቤት እፈልጋለሁ"አለችው  እየፈገገች።

"እሺ እጄ ላይ ሶስት አማራጮች አሉ...አንደኛ የማውቀው  ትልቅ  ሆቴል  አሁን ደውዬ አልጋ ልይዝልሽ እችላለሁ...ሁለተኛ ለሠገን ደውዬላት ቤት ልወስድሽ እችላለሁ።ሶስተኛ ሲ.ኤም.ሲ የሚገኝ አንድ ሪል ስቴት ላይ ሁሉ  ነገር የተሟላለት የድርጅቱ አፓርታማ አለ፤ቁልፉ ስላለኝ እዛ ላደርስሽ እችላለሁ።

"ላስብበት"

"አዳማ እስክንደርስ አስቢበት"

ከዛ ሁለቱም በየገዛ ሀሳባቸው ውስጥ ስለገቡ ፀጥታ ሰፈነ።ወደቤት ያላትን አልተመቻትም።በዛን ሰዓት ሰገን የተባለችውን ጥብቅና ረቂቅ ልጅ ለማግኘት ዝግጁ አልነበረችም። የተሻለውና ምቾት የሚሰጣት አፓርታማው ነበር፤ግን ፈራች፡፡የፈራችው ቁልፉ  እኔ  ጋር  አለ  ስላላት  ነው።አስገብቷት  ቁልፉን  አስረክቧት ደህና አደሪ በማለት ወደማደሪያው ይሄዳል ወይስ ሊተናኮላት ይሞክራል? እንደዛ ካደረገ ደግሞ ውጤቱ ጥሩ አይሆንም..ከስራ ባለደረባዋ  ጋር ገና በመጀመሪያዎቹ ቀናቶች መቃቃር በቀጣይ ፈተናዋ የበዛ እና  ይበልጥ ውስብስብ ማድረግ ይሆንባታል። እንደዛ አብጠርጥራ የሁሉንም ምርጫ ጉዳት ጥቅሙን ካሰላች በኃላ ድንገት"ሆቴል ያዝልኝ‹‹ነበር  ያለችው፡፡››በጣም የሚገርመው ያንን ቃል የተናገረችው ልክ አሁን  መኪናዋን እየነዳች በደረሰችበት ቦታ ሲደርሱ ነበር፤ እርግጥ ያን ጊዜ በግራዋ በኩል  ተንጣሎ የሚታየው የወንጂ ስኳር ፍብሪካ ንብረት የሆነው ሸንኮራ አሁን እያየች ካለው የበለጠ ረጅምና ለቆረጣ የደረሰ ነበር፡በወቅቱ ምርጫዋን ከሳወቀችው በኃላ መኪናውን መንዳቱን ሳያቋርጥ ስልኩን ከዳሽ ቦርድ ላይ አነሳና ቁጥሩን ፈላልጎ ደወለ።
"እ.ሜሮን.ሰላም.ነሽ"
"ደህናነኝ…››
‹‹አንድ አልጋ ፈልጌ ነበር" "አዎ..ለትልቅ እንግዳ  ነው"
"አመሠግናለሁ"ብሎ ዘጋውና ስልኩን በማስቀመጥ...አሁን የት አድራለሁ ብለሽ ማሰብ የለብሽም..ከዛ ይልቅ ይሄን ልጅ እራት እጋብዘዋለሁ ወይስ ቤተሠቦቼ የጋበዙት ይበቃዋል የሚለውን አስቢበት።"አላት
‹‹ኧረ አንተ ብቻ ፍቃደኛ ሁን እንጂ እጋብዝሀለሁ"አለችው።

"ስቀልድሽ ነው"አለ

💫ይቀጥላል💫

ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube 

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍7813🔥2
አትሮኖስ pinned «#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ ፡ ፡ #ክፍል_አስራ_ሰባት ፡ ፡ #በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ ሳባ የአሰላን ከተማ ለቃ እንደወጣች በደመነፍስ ነበር ስትነዳ የነበረው፡፡ ሀሳቧ ሁሉ ወደኃላ ተመልሷል..ያንን የተረገመ ስራ እንዴት እንደ ጀመረች አስር  አመት ወደኃላ ተመልሳ ማብላላት ጀመረች፡፡ ከ10 ዓመት በፊት ያኔ በዛ ዘመን አዲሱን ስራዋን ለመጀመር ከሰገን  ጋር የመጨረሻ ድርድር ስታደርግ እና ሲለያዩ አንድ ምክር ሰጥታት…»
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ሁለት  ተኩል  ላይ  ወሎ  ሰፈር  የያዘላት  ሆቴል ጋር  ደረሱ፤ክፍልአስገባት።
‹‹ሌላ የምትፈልጊው  ነገር አለ ?›
"ኧረ ቤተ- መንግስት ነው የተከራየህልኝ...ካልደበረህ ሆቴል የሆነ ነገር እየተጠቀምክ ትጠብቀኛለህ...ምቾት እየተሠማኝ ስላልሆነ ሻወር ለመውሰድ 10 ደቂቃ ይበቃኛል።
‹‹እንዴ አመረርሽ እንዴ…?እኔ እኮ ደህና እደሪ ብዬሽ ወደቤት ልሄድ ነበረ"
‹‹ምነው ቤት ይጠብቁሀል እንዴ?"
"አዎ አጥሩን ስከፍት እያንቧረቀ የሚቀበለኝ አንድ ውሻ አለኝ" "በቃ?"
"አዎ...በቃ...ለማንኛውም ታች እንገናኝ።" ብሏት ወጥቶ በሩን ዘጋና ሄደ፡፡ እሷም እየቀነቀነ ያስቸገረትን ሰውነቷን ለመታጠብ ወደ ሻወር አመራች። ሰውነቷን ታጥባ ጨርሳ በሻንጣዋ ከያዘችው ቅያሪ ቀሚስ ምርጥ ያለችውን ቀሚስ ለብሳ የብር ቦርሳዋን ይዛ ክፍሏን ቆለፈችና ወደታች ወደ ሆቴሉ ወረደች፡፡
ምግብ አዳራሹ ውስጥ ገብታ ዞር ዞር እያለች ብትፈልገው ልታገኘው አልቻለችም።ወደ ባሩ ስትገባ ባለጌ ወንበር ላይ ተቀምጦ መጠጡን ይልፋል፡፡ እንዳየችው ፈራ ተባ እያለች ወደ እሱ ቀረበች።መምጣቷን ሲያይ ከመቀመጫው ላይ ተንሸራቶ በመውረድ ተቀበላት።

‹‹ቆየሁብህ እንዴ?›

"አይ እንደውም ፈጠንሽ...ነይ መጀመሪያ እራት እንብላ"

ተከተለችው...፡፡ ሲገቡ አስተናጋጇ ወደተያዘላቸው ወንበር እየመራች ወሰደችና አሰቀመጠቻቸው። ሜኑ መጣና አዘዙ ፡፡ቆንጆ እራት በሉ፡፡ሂሳብ ለመክፈል እሷ ወደቦርሳዋ እጇን ከመስዳዷ በፊት እሱ ቀድሞ ዘጋ"የከፈለውን  ብር  ገርመም አድርጋ ስታየው ተገረመች..
‹‹ይሄ ሰውዬ  እውነት  ሹፌር  ብቻ  ነው?››ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡  መልስ ሳታገኝ ወደባር ይዟት ገባ ።ሁለቱም የየምርጫቸውን አዘው አየተጎነጩና በጫወታ እያዋዙ ጊዜውን መግፋት ጀመሩ።ሳባ በማታውቀው ምክንያት ደስ እያለት መጣ ...ሞቅ እያላት ሲመጣ እያቅበጠበጣት መጣ..በቀደም ሰገን ስትሸኛት የተናገረቻት የመጨረሻ ምከር ከምናቧ ሊጠፋ አልቻለም። እንደዛ ብታደርጊ ይሻላል ...እዚህ አንፈልገውም"አዎ ቃል በቃል ባይሆንም እንደዛ ነበር ያለቻት፡፡ እናም ምክሩን ተቀብላ በሚቀጥሉት ሶስት ቀናት ውስጥ ለወራት ከተኳረፈችው ፍቅረኛዋ በመታረቅ ምክሯን ተግባራዊ ለማድረግ እቅድ ነበራት። ግን አሁን አላስቻላትም።በዛን ሰዓት ከኮተቤ ተነስቶ ወሎሰፈር መምጣት እንደማይችል ብታውቅም ቢያንስ ድምፁን ለመስማት ፈለገች...ለወራት ሲደውልላትና ይቅር እንድትለው በአማላጅ ጭምር ሲማፀናት ነበር..ተስፋ ቆርጦ ግንኙነታቸውን ሁሉ እርግፍ አድርገው  ያቆሙ ከመሰሉ ወር ደፍኖ ነበር "መቼስ አሁን ስደውልለት በርሬ ካልመጣሁ ብሎ ያስቸግረኛል" ስትል ተስፋ አደረገች፡፡
  "ጨክኖ ካልመጣሁ ካለ መቼስ ምን አደርጋለሁ...ለማንኛውም  ልደውልለት" በማለት ወሰነችና"ቶይሌት ደርሼ ልምጣ?"ብላ ለደምሳሽ በመናገር ከተቀመጠችበት ተነሳች።
"ድረሺና ነይ..ሰዓት እየሄደ ስለሆነ ስትመጪ ወደክፍልሽ አድርሼሽ እሄዳለሁ"አላት።
    እሷም ከቦርሳዋ ገንዘብ ዛቅ አደረገችና ጠረጴዛ ላይ ወርወራ‹‹..እንግዲያው ሂሳብ ዝጋና ጠብቀኝ...ራስ ወዳድ ሆኜ አስመሸሁብህ አይደል..?››ብላ ከእሱ መልስ ሳትጠብቅ ቦርሳዋን እዛው ጠረጴዛ ላይ ጥላ ስልኳን ብቻ  በእጇ  ይዛ እየተውረገረገች በሆቴሉ የኋላ፣በር ወደውስጥ ገባች...ወደ ቶይሌት እየተራመደች ደወለች...መጥራት ሲጀምር ሰውነቷን ፍርሀት ወረራት
"አሁን ምን እለዋለሁ?"ጨነቃት...ደግነቱ ስልኩ አልተነሳም...
ጥሪውን ጨርሶ ተቋረጠ። የምታደርገው ግራ ገባት፡፡ ሰዓቱን አየች። ለአምስት ሰዓት አስር ጉዳይ ይላል።

‹‹ያ እንቅልፋም በዚህ ሰዓትማ  ሀይለኛ  ህልም  እያለመ ነው"ስትል  አሰበች ቶይሌት ገባችና የከፈተችውን በራፍ መልሳ ዘግታ ቀሚሷን ገልባ ፓንቷን ወደታች አንሸራታ ቁጭ አለች። ሽንቷ ወጥሯት ተጨናንቃ ነበር...
ሿሿሿ ብሎ መውረድ ጀመረ.. በዚህ መሀል ስልኳ ጠራ…አየችው።ራሱ ነው።

‹‹ይሄ  እንቅልፋም  ነቃ  ማለት  ነው....ልታነሳ  ፈለገች ...የሽንቷ  የሿሿታ  ድምፅ እሱ ጆሮ ደርሶ እንዳይረብሸው እስክትጨርስ መጠበቀ ወሰነች  ...ሽንቷን ከማጠናቀቋ በፊት ስልኩ ተቋረጠ...""ከሁለት ደቂቃ በኃላ ራሷ ደወለች።ተነሳ።
   ጆሮዋ ላይ ለጥፋ ፀጥ አለች።‹‹አዎ እኔ የመናገር እድሉን ካመቻቸሁለት ይበቃል..ይቅርታ የመጠየቅ ጥፋቱን እየተናዘዘ የመለማመጥና የመለመን ድርሻው የእሱ መሆን አለበት።አዎ  እኔ መልስ  የመስጪያ  ጊዜዬ እስኪደርስ በኩራት መጠበቅ ነው ያለብኝ›› ብላ በዝምታዋ ፀናች።ክፋቱ ከዛም ወገን ፈጣን መልስ አላገኘችም፡፡

ከረጅም ጥበቃ በኋላ "ሄ....ሎ"የሚል ድምፅ ከወዲያኛው ጫፍ እየተንሳፈፈ መጥቶ ጆሮዋ ውስጥ ተሰነቀረ....ውርር አደረጋት።ቶሎ ብላ ከጆሮዋ አነሳችና ወደ አይኗ አቀረበችው፤አፍጥጣ እና አትኩራ አየችው።አልተሣሣተችም ስሙም  ቁጥሩም የራሱ ነበር።
"ሄሎ የእሱባለው ስልክ አይደለም እንዴ?"
"ትክክል ነሽ..አልተሳሳትሽም...ግን አንቺን ማን ልበል?"
"አይ አታውቂኝም...እሱን ልታቀርቢልኝ አትቺይም...ነው ወይስ ተኝቷል?"ስትል ጠየቀቻት
‹‹አዎ ቁጥሩን ካልተሳሳትኩ የምታናግረኝ እህቱ ነች ማለት ነው›› ስትል ነበር በእርግጠኝነት የወሰነችው።ከልጅቷ የሰማችው መልስ ግን የሚያጥወለውል አይነት ነበር።
"አይ አልተኛም ልጅ እያባበለ ነው?"
‹‹እንዴ የምን ልጅ?"
"የምን ልጅ ማለት ምን ማለት ነው..?የራሱን ልጅ ነዋ..የወለደውን" "ይቅርታ አንቺን ማን ልበል...?"
"ባለቤቱ ነኝ...በጣም አስቸኳይ ካልሆነ  "
ልጅቷ ተናግራ ሳትጨርስ ስልኩ ከእጇ ተንሸራቶ ወለሉ ላይ   ወደቀ፡፡ከውጭ‹‹ሳባ..የት.ነሽ....?"የሚል ተደጋጋሚ ጥሪ ስትሰማ ነበር ከድንዛዜዋ የባነነችው፡፡
"እ....መጣሁ"አለችና ከሽንት  ቤቱ ሰሀን ተነሳችና  ፓንቷን  ወደ ላይ ጎትታ የነበረበት ቦታ በመመለስ ቀሚሷን ወደታች ለቀቀች።ጎንበስ አለችና የወደቀውን ሞባይል አነሳች።ስክሪኑ ከዳር ሰንጠቅ ብሏል።በክህደት ምክንያት ልቡ ከመሀል ለተሠነጠቀ ሰው የሞባይሉ መሰንጠቅግድ   ይሰጠዋል?።የሽንት ቤቱን በራፍ ከፍታ ስትወጣ ደምሳሽ ግራ በመጋባት በራፍ ላይ ቆሞ ሲጠብቃት አገኘችው።
   እንዳያት "እንዴ ምነው...?አመመሽ እንዴ?"ሲል ጠየቃት
ፍርጥም ብላ ‹‹ምነው"
   አይ ቆየሽ...ደግሞ ፊትሽ ተቀያይሯል...ይሄው ቦርሳሽ...ነይ ክፍልሽ ላድርስሽ"
    "አይ ወደ ክፍሌ መግባት አልፈልግም"ያልጠበቀው መልስ ስለነበረ ግራ ገባው "እ ምነው? በሰላም?"
ቦርሳዋን ተቀበለችውና ወደባር እየተመለሰች..."መጠጣት ፈልጋለሁ...ለዛውም በጣም"አለችው። ከኋላ ተከተላት...ከተነሱበት ቦታ ተመልሳ ተቀመጠችና አስተናጋጁን በእጇ ጠራችው።አስተናጋጁ ተንደርድሮ ስራቸው ሲደርስ ደምሳሽም ደርሶ ለመቀመጥ ወንበር እየሳበ ነበር...የቤቱን ምርጥ የተባለ ወይን አምጣልኝ...ደግሞ የሚያሰክር መሆን አለበት"አስተናጋጁ  ትዕዛዙን  ተቀበለና  በፍጥነት ተመልሶ ሄደ ።››
‹‹ይቅርታ ትንሽ መጠጣት ስለምፈልግ ነው።አንተ ሂድ...እዚሁ ጠጥቼ እዚሁ ክፍሌ መግባት የሚከብደኝ ይመስልሀል?።"

"ለእኔ.አታስቢ..እኔ.በማንኛውም.ሰዓትመሄድ.እችላለሁ...ለምጄዋለሁ"
እንግዲያው እንዳልክ"
"መጠጡ መጣና ተቀዳላት...እሱ ግን የጀመረውን  ቢራ አስመጣና  በመጠጣት የእሷን ሁኔታ በንቃት መከታተል ቀጠለ።
👍786🥰1
"ውይግን.ወንዶች...ስታስጠሉ"አለች ፈገግ አለ
"ይቅርታ አንተን ለመናገር ፈልጌ  አይደለም፤በአንድ ውሻ ስለተበሳጨሁ ነው"
   "ችግር.የለውም፣ገብቶኛል››አላት።ሴቶች.እንዲህ.አይነት ቃላት ከአንደበታቸው የሚያወጡትና እንዲህ አይነት ምሬት ውስጥ የሚገቡት ምን አይነት ሁኔታ ሲያጋጥማቸው እንደሆነ ከልምድ ጠንቅቆ ያውቃል።
"ገብቶኛል.ስትል...ምንድነው የገባህ?"
"የፍቅር ጉዳይ መሆኑ"
"ትክክል ነህ..አይገርምህም...እኔ እሱን ብዬ ስንት እድል አሳልፌ ስንት ጊዜዬን አጥፍቼ ባለትዳር…ጭራሽ የልጅ አባት መሆኑን አልሰማም።››
"አንዳንዴ  ያጋጥማል...ከመፅናናትና  እራስን  ከማጠንከር  ውጭ  ምን  ማድረግ ይቻላል።"
"እሱስ እውነትህን ነው..ለእሱ ሀዘኔም እንባዬም አይገባውም...እንደዛ  ሲለምነኝ እሺ ብዬው አስረክቤው ቢሆን ተንገብግቤም አላባራ ነበር።››
"ምኑን"ግራ ገብቶት ጠየቃት።

በንዴት መጠጡን በላይ በላይ ስትለጋው ወደስካር እየሄደችና አፏም እየተንተባተበ ነው‹‹ምኑን ይመስልሀል...?››አለችው…፡፡ብርጭቆዋን አንስታ አንዴ  ገርገጭ አድርጋ ጠጣችና ንግግሯን አራዘመች‹‹…. ለማንኛውም ከዚህ የጨፈገገ ስሜት እራሴን ለመታደግ መጠጣት ነው የምፈልገው..... ጠጣ እንጠጣ...እንደሰት ..እናም እንጨፍር።››

"እሺ እንደንሳ"ብሏት ይዞት ተነሳና በዳንስ ወለሉን ከሞሉት ጥንዶች መካከል ይዟት ገባ። ደረቱ ላይ ልጥፍ ብላ በጠንካራና ፈርጣማ ክንዶቹ ወገቧን አቅፎ ከሰውነቱ እያጣበቃት ..ደግሞም እየለቀቃትና ጣቶቿን ይዞ እያሽከረከራት እክትዝል አስደነሳት፤እያረፉ እየጠጡ ዘፈን ሲቀየር እየተነሱ እየደነሱ ሰባት ሰዓት ላይ ሙሉ በሙሉ ከቁጥጥር ውጭ ሆና ተዝለፈለፈችና ማን መሆኗን እስክትረሳ ድረስ ራሷን ሳተች።

እሱ ግን ምንም እንኳን ቢሰክርም በቂ ልምድ ስላለው ብዙም አልተቸገረም። ሂሳብ ከፈለና እሷን ደግፎ ከባሩ የመጎተት ያህል እየሳባት ቢወጣም መኝታ ቤቱ ወደሚገኝበት  ፎቅ  ይዞት   ሄደና   ሊፍቱ   ውስጥ   አስገባት..ሲደርሱ ግን ሊፍቱ ቢከፈትም መንቀሳቀስ አልቻለችም፡፡ ሰቅስቆ ሙሉ  በሙሉ ወደላይ በማንሳት አቀፋት።እና ወደክፍሏ ተሸክሞ ወሰዳት፡፡ ካርዱን ከቦርሳዋ አወጣና ከፈተ.. መልሶ ዘጋው….አልጋ ላይ አስተኛት።የለበሰችውን ልብስ እያገለባበጠ መጀመሪያ ጫማዋን አወለቀ፡፡ከዛ እያገለባበጠ ቀሚሷን አወለቀላት "ሮዝ ቀለም ያለው ከመቀመጫዋ የተጣበቀ ፓንት እና ተመሳሳይ ቀለም ያለው ጡት ማስያዣ ብቻ እላዯ ላይ ቀረ.፡፡ ሻንጣዋን ከፈተና ፒጃማ ፈለገ ስስ ደማቅ ቀይ ፒጃማ አገኘ….መጀመሪያ አንገቷን ቀና አደረገ…አጠለቀላት፡፡ ከዛ ወደታች እየጎተተ እጆቿን አስገባና ሙሉ በሙሉ አለበሳት...ከዛ አቀፈና ብርድ ልብሱን በመግለጥ ከውስጥ አስገባት…ያወለቀላትን ቀሚስ በስነስርዓት አጣጥፎ አልጋው ጎን ያለው ኮመዲኖ ላይ አስቀመጠና ወደ ሶፋው ተጓዘ ..ጫማውን ብቻ አወለቀና ጎኑ ላይ ሽጦ የነበረውን ሽጉጥ በማውጣት ከትራሱ ስር በማሰቀመጥ እግሩን ዘርግቶ እጆቹን አጣጥፎ ቀን ለብሷት በዋለው ልብስ ከላይ ምንም ሳይለብስ ተኛ...እሱም ቀኑን ሙሉ ሲባክን ስለነበረና አሰላ ደርሶ መመለሱም ስላንገላታው ወዲያው ነበር እንቅልፍ የወሰደው።

💫ይቀጥላል💫

ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube 

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍6113
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ


#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ለሊት 10 ሰዓት  ነበር የባነነችው። ራስ ምታት  እየወቀራት  ነበር።  አይኗን እንኳን መግለጥ አቅቷታል።"የት ነው ያለሁት ?"እጇን ወደአይኖቿ ላከችና እያሻሸች ከመኝታዋ ተነሳች።...ሽንቷ  ነው  ከእንቅልፏ  የቀሰቀሳት፡፡ከአልጋዋ   ወረደችና ቀጥታ ወደሽንት ቤት ሄደች። ጨርሳ ስትመለስ ከእንቅልፏ ድባቴ ሙሉ በሙሉ ነቃታ.. አይኖቿም ተከፍተው ነበረ...መኝታ ክፍሏ  ውስጥ ባለው  ሶፋ ላይ የተኛ ሰው አለ..አፍጥጣ አየችው…አልጋ ልብስም ሆነ ሌላ ስላለበሰ ወዲያው ነው ማንነቱን የለየችው። እሱም ነቅቶ በዝምታ እያያት ነው።

"እንዴ ደምሳሽ...?"አለችው በመገረም

"ይቅርታ በእንደዛ አይነት ሁኔታ ብቻሽን  ጥዬሽ  መሄድ  አልቻልኩም...ምን አልባት ለሊት ካመመሽ ብዬ ሰጋሁ››
"ታዲያ ቢያንስ አልጋ ልብሱን ወስደህ አትለብስም ነበር?"አለችው አልጋው  ጠርዝ ላይ ተቀምጣ።

"አይ ችግር የለውም...በእንደዚህ አይነት ሁኔታ የመተኛት  የብዙ  ጊዜ  ልምድ አለኝ"

"ቢሆንም ለእኔ ስትል እንዲህ  በብርድ  መመታት የለብህም ››አለችና  አልጋ ልብሱን ከላይ በማንሳት አልብሳው ስትመለስ ማታ ለብሳው የነበረውን ቀሚስ በስርአት ተጣጥፎ ተቀምጦ አየች። ለመጀመሪያ ጊዜ  የለበሰችውን  ቢጃማ አስተዋለች

"መቼ ነው ቢጃማዬን የቀየርኩት?"ራሷን ጠየቀች...ለማስታወስ ሞከረች...ትዝ ያላት ነገር የለም...ደግሞ ቀሚስ አስተጣጠፏ የእሷ አይደለም። እንኳን ሰክራ በሰላሙም ቀን እንዲህ አይነት ነገር ላይ ሰነፍ ነች።አልጋ ላይ ወጥታ በተገለጠው ብርድ ልብስ ወደውስጥ ገብታ እየተኛች"ደምሳሽ"ስትል ተጣራች።
"አቤት"
"ልብሴን ማን ነው ያወለቀልኝ?" "ምነው የተበላሸ ነገር አለ እንዴ?"
"አይ ማለቴ..."የምትለው ጠፋት
"በይ ወደ እንቅልፍሽ ተመለሺ ...ለሊት ነው"

"እሺ ደህና እደር"አለችውና ሙሉ በሙሉ ተሸፈነች፤እንቅልፍ ግን ሊወስዳት አልቻለም።ማታ በፍቅረኛዋ ልብ ሰባሪ ድርጊት ልቧ እስኪሰባበር ድረስ አዝናና ተበሳጭታ ነበር።በዛም የተነሳ አቅሏን እስክትስት ጠጥታ ይሄው ለሳምንት ብቻ የምታውቀው ባዕድ ሰው ልብሷን አውልቆ መላ እርቃኗን አገላብጦ አይቶ ሌላ ልብስ አልብሶ እስኪያስተኛት የምታውቀው  ነገር  አልነበረም።  በቀጣይነት  ከእሱ ጋር እንዴት አድርጋ ነው ስራ የምትሰራው?። እሷን ባያት ቁጥር እርቃኗ ነው የሚታየው።"ቆይ ግን ሌላ ነገር አድርጎኝ ይሆን እንዴ?"
ይሄ ሀሳብ ወደምናቧ በመጣበት ቅፅበት በርግጋ ከመኝታዋ ተነስታ ቁጭ አለችና ብርድ ልብሱን ከላዯ በመግፈፍ እግሯን አንፈርክካ ጭኗ መካከል አይኖቿን ተክላ ቀኝ እጇን በፓንቷ ስር ሰዳ መዳበስ ጀመረች...በዚህ ቅፅበት ደምሳሽ ከተኛበት በርግጎ እና ተንደርድሮ ስሯ ቆመና"ምን ሆንሽ ...ምን ነካሽ?" እያለ ይጠይቃት ጀመር…በሌላ ድንጋጤና እፍረት ቶሎ ብላ እጇን ከፓንቷ መዛ አወጣችና ቢጃማዋን ወደታች መልሳ .."እኔ እንጃ የሆነ አውሬ ማለቴ ትንኝ ምናምን ነገር መሠለኝ"አንደበቷ ላይ   የመጣላትን ቀባጠረች።

"አውሬ..እዚህ  አውሬ...እንዴት ተደርጎ...?እስኪ ተነሽ…ከአልጋ ውረጂ" እውነታውን  ብታውቅም    ትዕዛዙን  ተቀብላ  ወረደች    ..ልብሷን      ከአልጋው  ላይ በየተራ    በማንሳት  ማራገፍ  ጀመረ።ሳቋ    አፈናትም..አሳዘናትም። እየተንደረደረች ወደሻወር ቤት ገባች። ፓንቷን አወለቀችና ሙሉ በሙሉ በነፃነት ብልቷን ማየትና መፈተሽ ጀመረች...እና በሞኝ ድርጊቷ በራሷ ሳቀች።‹‹የሆነ ነገር አድርጎ ቢሆን በቀላሉ አላውቅም ነበር...?ለመጀመሪያ  ጊዜ  ያደረኩት ወሲብ  እንዴት   እንዲህ ቀላልና  ህመም  አልባ  ይሆናል?ብዬ  ላስብ  ቻልኩ….  ደግሞስ  ….አድርጎስ ቢሆን ምን ነበር የማደርገው?" ለራሷ ጥያቄ እራሷ መመለስ ጀመረች"አዎ በጣም ነበር የምበሳጨው "ስትል ለራሷ መልስ ሰጠች።
ደግሞ ሌላ ጥያቄ ‹‹ግን ለምንድነው የምበሳጨው?"

"ዋናው በህይወት ዘመኔ አንዴ ብቻ የማገኘውን ሳላጣጥመው ማጣቴ ያበሳጨኛል...ሁለተኛው  ያለፍቃዴ  ተሸውጄ  መሆኑ… ሶስተኛው... ››አለችና  ሀሳቧን  ገታች‹‹ሶስተኛ ለማላፈቅረው ሰው በመሆኑ››ልትል ነበር...ግን ልቧ እንቢ አላት…::በተወሰነ ደረጃማ ቢሆን ወዳው ነበር...በፍጥነት ወደውስጧ እየገባ ነበር። እና እሱ በመሆኑ የሚከፋት መስሎ አልተሰማትም..ከሀሳቧ ያወጣት  የሻወር ቤቱ መንኳኳት ነበር፡
"አቤት"አለች "ሰላም.ነሽ?"
በእጇ አንጠልጥላው የነበረውን ፓንት መልሳ በማጥለቅ  ፋንታ  ማንጠልጠያው ላይ ሰቀለችና.."ሰላም ነኝ …ሰላም ነኝ"እያለች በራፍን ከፈተችና ወጣች። ሰላም መሆኗን ለማረጋገጥ አይኖቹን ከላይ እታች አንከባለለባት።
"ትንሽ  ሲያሸልበኝ  ቃዠቼ  መሠለኝ"አለችና  ወደአልጋው  ስትሄድ  እንደአዲስ አስተካክሎ አንጥፎት ነበር ።
"አስቸገርኩህ አይደል?"
ወደ ሶፋው እየሄደ”አረ ችግር የለውም ዋናው ያንቺ ደህንነት ነው።” አላት "ለምን እዚህ አትተኛም… ይበቃናል"
የእሷን ግብዣ ችላ አለና አዲስ የወሬ ርዕስ ከፈተ "የሆነው ነገር ምን አልባት በምክንያት ነው"
"ምኑ?"
"ከምታፈቅሪው ሰው መለያየትሽ ..."አላት፡፡
"የማፈቅረውን  ሰው  በዚህ  መልክ  ማጣቴ  እንዴት  ነው  ጥሩ  የሚሆነው?"ግራ ተጋብታ ጠየቀችው።
"አየሽ ...እሱ ባይከዳሽም ውለሽ አድረሽ አንቺ ትከጂው ነበረ"
"አረ...እንደዛ አይነት ሰው እመስላለሁ?።››
"አንቺ በፍፁም አትመስይኝም...የጀመርሽው ስራ ባህሪ ግን እንደዛ ነው። በጥቂት ቀናት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ይቀይርሻል። ሌላ አመለካከት፤የተለየ    ስነልቦና ያለሽ አዲስ ሰው ነው የምትሆኚው። እና በምንም  አይነት   ፍቅረኛሽ እንደሚፈልግሽ አይነት ሰው ፍፁም ልትሆኚ አትችይም። ለተወሰነ ጊዜ ተጨቃጭቃችሁ ከዛ   መለያየታችሁ   አይቀሬ   ነበር..ልዩነቱ   አሁን   እሱ   ነው ልብሽን የሠበረው...ቢቆይ ኖሮ አንቺ ነበርሽ ልቡን የምትሰብሪው።››
"እንድፈራ እያደረከኝ ነው"
"ይቅርታ....እውነቱን እየነገርኩሽ እና ለሚመጣው ነገ እያዘጋጀሁሽ ነው"
"ለመሆኑ አንተ ፍቅረኛ የለህም?"
"ፍፁም.የለኝም...ወደፊትም አይኖረኝም" "እንዴ ለምን?"
‹‹እየነገርኩሽ  እኮ  ነው...እዚህ  ስራ  ውስጥ  ከአንድ  አመት  በላይ  ከቆየሽ ፍቅር...እምነት...ጋብቻ....ቤተሰብ የሚሉት ነገሮች ትርጉም ያጡብሻል።››

"በምን ምክንያት? "
"ልታይው አይደለ...ምን አስቸኮለሽ?...አሁን በይ ተኚ"
"እሺ ግን ነገ ካቆምንበት እንቀጥላለን"
"ችግር የለውም"
"ጥዋት ሁለት ሰዓት ከእንቅልፏ ስትባንን ክፍሉ ባዶ ነበር። መጀመሪያ  ወደሻወር ቤት የገባ መስሏት ነበር ...ግን ኮመዲኖ ላይ  በተወላት ማስታወሻ  ትቷት ወደጉዳዩ እንደሄደ ተረዳች።
የተወላት ማስታወሻ‹‹ሳባ...የሆነች ስራ ስላለችኝ ሄጄያለሁ።ስራዬን እስከ አራት ሰዓት እጨርሳለሁ።ከዛ በኋላ በፈለግሺኝ ሰዓት ደውይልኝ"ይላል።
//
አሁን…ዛሬ ላይ
አዲስ አበባ ሰፈሯ ስለደረስች ከትዝታዋ ወጣችና በራፉ እንዲከፈትላት የመኪናዋን ክላክስ አስጮኸች…አንድ ሰዐት ተኩል ሆኖ ነበር፡፡ዘበኛው ከፈተላት መኪናዋን ወደውሰጥ አስገባችና አቁማ ወረደች…፡፡
👍759👏2😁1
በእጁ መፅሀፍ ይዞ ከእሷ በአምስት ሜትር ርቀት ላይ ቆሞ….‹‹ሳባ ሰላም ነሽ?››አላት
‹‹አዎ ሰላም ነኝ፣ ምነው?››ስትል ጠየቀችው…ሁኔታውን ስታይ ምኑም ዘበኛ አይመስልም…25 ወይም 30 አመት ቢሆነው ነው፡፡የሚለብሳቸው ልብሶች ብራንድ ባይሆኑም ግን ሁሌ ፅድት ያሉ ናቸው…ፀጉሩ የአበሻ  አይመስልም፡፡ ለሁለት ተከፍሎ ግራና ቀኝ ድፍት እንዳለ  ነው፡፡ልቅም  ያለ  ቆንጆ  ሚባል ባይሆንም አይነግቡና ትኩረት የሚስብ አይነት ነው፡፡ከዚህ በፊት የነበሩት ዘበኞች ብዙ ጊዜ በዚህን ሰዓት ዱላ ይዘው ግቢ ውስጥ ሲንጎራደዱ ወይም ማደሪያቸው ፊት ለፊት ወንበር አስቀምጠው ሬዲዬ ሲያዳምጡ ነው የምታያቸው…እሱ ግን እሷ ቤት ከተቀጠረ ገና ሁለተኛ ወሩ ውስጥ ቢሆንም  ይሄው  ከመጣበት  ቀን አንስቶ ቀንም ሆነ ለሊት መፅሀፍ ላይ ተጣብቆ ነው የምታየው…
‹‹ይቅርታ ስለተዳፈርኩሽ..ድንገት እንደወጣሽ እኮ ለሶስት ቀን ስትጠፊ ምን አጋጥሟት ይሆነ ብዬ ሰግቼ ነበር?››
‹‹አይ ምንም አይደል…የቤተሰብ ጉዳይ አጋጥሞኝ ክፍለሀገር ሄጄ ነው..በል ደህና እደር ››
‹‹ደህና እደሪ››
ትታው ወደ ውስጥ ገባች፡፡ ቀጥታ ወደመኝታ ቤቷ ነው ያመራችው…የዘበኛው ጥያቄ አእምሮዋን እየበላት ነው…ከተቀጠረ ገና ሁለት ወሩ ነው…ስሙን እንኳን ሁለት ሶስቴ የነገራት ቢሆንም  አሁን  አእምሮዋ  ውስጥ  የለም.. ረስታዋለች፡፡ ወር ብትቆይ ትዝ ብሎት ስለእሷ ይጨነቃል ብላ በፍፁም ገምታ አታውቅም…የሁለት ቀን እንቅልፍ ስላለባት ወዲያው ነበር እንቅልፍ የወሰዳት

💫ይቀጥላል💫

ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube 

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍669
አትሮኖስ pinned «#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ ፡ ፡ #ክፍል_አስራ_ዘጠኝ ፡ ፡ #በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ ለሊት 10 ሰዓት  ነበር የባነነችው። ራስ ምታት  እየወቀራት  ነበር።  አይኗን እንኳን መግለጥ አቅቷታል።"የት ነው ያለሁት ?"እጇን ወደአይኖቿ ላከችና እያሻሸች ከመኝታዋ ተነሳች።...ሽንቷ  ነው  ከእንቅልፏ  የቀሰቀሳት፡፡ከአልጋዋ   ወረደችና ቀጥታ ወደሽንት ቤት ሄደች። ጨርሳ ስትመለስ ከእንቅልፏ ድባቴ ሙሉ በሙሉ ነቃታ..…»
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ


#ክፍል_ሀያ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


…..የሰላም እንቅልፍ አልተኛችም እንቅልፏ ያው እንደተለመደው በስቃይ እና በቅዠት የተሞላ እንቅልፍ ነበር…ስምንት ሰዓት ላይ ሙሉ በሙሉ ከእንቅልፏ ተነስታ ወደ በረንዳ ወጣች….ግቢዋ በፓውዛ መብራት ድምቅ ብሎ ነበር፤ግን ፀጥ ያለ ነው..ፀጥታው ደስ ያሰኛል፡፡ግን አየሩ ይቀዘቅዛል ..ወደውስጥ ተመለሰችና በለበሰችው የለሊት ፒጃማዋ ላይ ከአመት በፊት ስንዱ አሰርታ የሰጠቻትን ወፍራም ጋቢ ከቁም ሳጥኗ አውጥታ ለበሰችና ተመልሳ ወጥታ ወንበር ላይ ቁጭ አለች፡፡

እና ቅድም ከአሰላ ስትመጣ በመንገዷ ሁሉ ስታመነዥገው የነበረው ትዝታና በራፏ ጋር ስትደርስ አቁማ ነበር፡፡ከሰአታት.እረፍት በኋላ አሁን በእኩለ ለሊት ካቆመችበት ቀጠለች፡፡
ትዝታ…ከአስር አመት በፊት
ከዛሬ አስር አመት በፊት የነበረችው ሳባ ናፈቀቻት፡፡ እስከዚያ  ጊዜ  ድረስ የዋህ፤ንፁህ ግን ደግሞ ጉጉና ደፋር ወጣት ነበረች፡፡ለአባቷ ያላት ፍቅር በወቅቱ ምንም አይነት መስዋዕትነት ለመክፈል እንዳታመነታ አድርጓታል፡፡ ቢሆንም በወቅቱ የነበራት ምልከታ በአስር አመት ውስጥ ከሆነው ፍፁም  የተለየ  እና የምድር እና የጨረቃን ያህል ርቀት ያለው ነው፡፡ በወቅቱ ሀሳቧም ግልፅ ምኞቷም ቅልብጭ ያለ ነበር፡፡ምንም አይነት ስራም ቢሆን ሰርታ ገንዘብ በማግኘት ለአባቷ ዘመናዊ ዊልቸር መግዛት ከዛም አሪፍ መኪና ገዝቶ ምቹ ህይወት እንዲኖር ማድረግ…ከዛ በቃ ወደኃላ ተመለሳ እንደቀድሞ ንፁህ ቀላልና የተለመደ አይነት ህይወት መኖር…እንደዛ ነበር እቅዷ….ግን ለካ ወደኋላ መመለስ ወይንም ባሉበትም ቢሆን ቆሞ የህይወትን  ፍሬን  በመያዝ  ከገቡበት ማጥ መውጣት ቀላልስራ.አልነበረም…ይሄው አስር አመት ፈጀባት፡፡
በወቅቱ ከደምሳሽ ጋር አንድ ቤርጎ ውስጥ ካደሩና ጠዋት  እሱ  በተኛችበት ማስታወሻ ትቶላት ከሄደ ቡኃላ አልጋዋን ለቃ በመውረድ ልብሷን በጥንቃቄ ለብሳ እዛው ሆቴል ቁርሷን  በልታ  ወደለቀቀችው  መስሪያ  ቤቷ  ነበር የሄደችው፡፡ቀኑን ሙሉ እጇ ላይ ያሉትን የድርጅቱን ንብረቶች ስታስረክብ...ከዛም ክሊራንስ በየዲፓርትመንቱ እየዞረች ስታስፈርም...እንዲሁ ስትባክን ነው የዋለችው፡፡ እዛው እያለች ከቀኑ 10 ሰዓት ሞላ። ሰዓቱን ያየችው እየጠራ ያለውን ስልኳን ለማንሳት ከቦርሳዋ ስታወጣ ነበር።
"ሄሎ ደምሳሽ...እንዴት ዋልክ?"

"ደህና ነኝ...ነፃነትሽን ላለመጋፋት ነበር እስከአሁን ያልደወልኩልሽ...ግን ስጠፊ አላስቻለኝም፡፡"

"አረ ሰላም ነኝ፤መስሪያ ቤት ነው ያለሁት…ክሊራንስ ለመጨረስ እየተሯሯጥኩ ስለነበረ ነው...ለመደወል ምንም ጊዜ አልነበረኝም"
"እና አሁንም አልጨረስሺም?"
"አይ አሁን እንኳን ወደመጨረሱ ነኝ..የሥራ ልምድ ተፅፎልኛል...መዝገብ ቤት ገብቶ ወጪ እስኪሆን ነው እየጠበቅኩ ያለሁት።››
"እንደዛ ከሆነ በቃ መጣሁ...ቅርብ ቦታ ነኝ..አንድ 15ደቂቃ ቢፈጅብኝ ነው።"ብሎ ስልኩን ዘጋው።ደስ የሚል ስሜት ሰውነቷን ወረራት።እንዲህ የሚያስብላት፤እንዲህ የሚንከባከባት ሰው ከጎኗ በመኖሩ ተደሰተች። እርግጥ ስራው ነው…ታውቃለች፡፡እሱም ደጋግሞ ነግሯታል። እሷ ግን እንደዛ እየተሠማት አይደለም። አሳቢነቱ ከልብ የመነጨ፤እንክብካቤው.ፍቅር የተቀየጠበት እንደሆነ ነው እየተረዳች የነበረው። ውስጧ በሰው ሲተማመን ከአባቷ ቀጥሎ የመጀመሪያው ሰው ነው። የምታፈቅረው የነበረውንና ልቧን የሰበራት ሰው ራሱ አብራው ባለችበት ጊዜ ሳይቀር እንደዚህ እንዲሰማት አድርጎ አያውቅም።
መኪና ውስጥ ገቢና ከጎኑ ተቀምጣ እያወሩና እየተጫወቱ እየተጓዙ ነው። "አሁን የምትሄጂበት ቦታ አለ?"ሲል ነበር የጠየቃት፡፡
"አይ የትም አልሄድም...በእለቱ  መስራት  የምፈልገውን.ስራ ጨርሼያለሁ...የምትሄድበት ቦታ ካለህ ሆቴል ጣል አድርገኝና መሄድ ትችላለህ፡፡"
"አይ እንደዛ ለማለት ፈልጌ አይደለም..የማትቸኩይ ከሆነ ቤቴ በሚቀጥለው ቅያስ አጠፍ ብሎ ስለሆነ ጎራ ብለን ልብስ ብቀይር ብዬ ነው"
"ታዲያ ምን ችግር አለው"
‹‹እንግዲያው እሺ››አለና መኪናዋን ወደ ግራ ጠመዘዘና በጠባብ ኮብል መንገድ ገባ…ትንሽ ከተጓዘ በኋላ ባለጥቁር ቀለም የብረት በራፍ ቪላ ቤት የመኪናዋን አፍንጫ አስጠጋና ጡሩንባዋን አስጮኸ...በፍጥነት በዘበኛው አማካይነት በሩ ተከፈተለትና ወደውስጥ ገባ..፡፡
"እዚህ ተከራይቶ ነው የሚኖረው ማለት ነው?"ብላ አሰበች፡፡ የዘበኛው መሽቆጥቆጥ ግን ግራ አጋባት፤ ከመኪና እንደወረደ ግዙፍ ሰንሰለት አንገቱ ላይ የተጠለቀለት ውሻ ሰንሰለት ለመበጠስ በሚፈልግ አይነት እየቦረቀ እና እየዘለለ ወደ ደምሳሽ አቅጣጫ ይዘል ጀመር..ሳባ በፍራቻ ወደ ኃሏ ሸሸች...ደምሳሽ በፈገግታና በደስታ ወደውሻው ተራመደ ስሩ ደረሰና፣ ጭንቅላቱን ሲያሻሽለት ውሻው ከድምፁ ቀነስ ከዝላዩ ሰከን እያለ መጣና እግሩ ስር ውልምጥምጥ ብሎ ተኛ…ከዛ የደምሳሽን እግር በረጅም ምላሱ ይልስ ጀመር፡፡
"መክሰሱን.ሰጠኸው?"
‹‹አዎ ጌታዬ አሁን በላ››
"በል  ጌታው  እንግዳ  አለብኝ"አለና  ከስሩ  ተነስቶ  ሳባን አስከትሎ  ወደግዙፉ  ቪላ ቤት ይዟት ገባ...
ቤቱ ቢያንስ 10 አባላት ያሉትን ቤተሰብ ዘና ባለ ሁኔታ ማኖር የሚያስችል ሁሉ ነገር የተሟላለት ባለብዙ ክፍል ግዙፍ ቤት ነው።

ወደ ሶፋው በእጁ እያመለከተ "ቁጭ በይ" አላት...በዝምታ የቤቱን ዙሪያ ገባ እየቃኘች ወደ አመለከታት ቦታ ሄዳ ቁጭ አለች።
"የሚጠጣ ምን ላምጣልሽ?"
"ያለውን.."
ተራመደና ሳሎን  ውስጥ ያለውን ግዙፍ ፍሪጅ ከፈተ...እንደ ሱፐርማርኬት ፍሪጅ ጥቅጥቅ ብሎ በመጠጥ አይነቶች፣በፍራፍሬና፣በታሸጉ ምግቦች ተሞልቷል። ሁለት ቢራ አነሳና ከመክፈቻ ጋር በማምጣት ከፍቶ አንድ ለእሷ አቀረበላትና ሌላውን በመክፈት ገርገጭ ገርገጭ በማድረግ ሩቡን ያህል ከላፈለት በኋላ ጠረጴዛው ላይ በማስቀመጥ ሪሞት በማንሳት ቲቪ ከፍቶ ሪሞቱን ለእሷ አቀበላትና፡፡ "ጥቂት ደቂቃ...ልብስ ቀይሬ ልምጣ፡፡"አላት፡፡
"ችግር የለውም…ኸረ ...ዘና ብለህ ቀይር፡፡ "ስትለው ወደ ውስጠኛ ክፍል አመራ...ከ10 ደቂቃ በኃላ ለብሶት የነበረውን ጥቁር ሱፍ አውልቆ ሰማያዊ ጅንስ ሱሪ በነጭ ቲሸርትና ከቡኒ ሌዘር ጋር ለብሶ ይበልጥ ፈርጣማና ጎረምሳ መስሎ ወጣ፡፡
"አልደበረሽም አይደል?"እያለ ከፊት ለፊቷ ተቀመጠና ጀምሯት የነበረውን ቢራ አንስቶ ተጎነጨ‹‹ኸረ የምን መደበር....ቤትህን  ገና መቼ አይቼ ጨረስኩት"
"እንዴት ነው ቤቴ ያምራል?"
"ያምራል...ቤተመንግስት አይደል እንዴ የሚመስለው...ግን እርግጠኛ ነህ ብቻህን ነው የምትኖረው?"
"አይ እንዳየሽው ዘበኛዬ አለ...ውሻዬም አብሮኝ ነውየሚኖረው  ..በየሁለት ቀን እየመጣች ቤት የምታፀዳልኝና ሌሎች ስራዎች የምትሰራልኝ ልጅም አለች፡"

"በቃ?"
"ምነው….ካነሰ እያየን እንጨምራለን፡፡" "የእውነት.ይገርማል...ግንኪራዩን ትችለዋለህ"
"የራሴ እኮ ነው"
"ዋው...!!"
"ይገርማል"
"አዎ..በጣም ያስገርማል....ብታከራየው እኮ በወር ከ50 ሺ ብር በላይ ያስገኝልሀል"
"ነው ግን...እኔ እንዲህ ዝግጁ ሆኖ እንዲቀመጥ ነው የምፈልገው …አንድ ቀን የማገባት ልጅ አግኝቼ ልቤ ሲፈቅድ ቶሎ ብዬ ሀሳቤን ሳልቀይር ጎትቼ ማስገባት ነው የምፈልገው።
"በንግግሩ ሳቋን ለቀቀች ‹‹ለመሆኑ እዚህ ስራ ላይ ስንት አመት ቆየህ?"
👍697👏2
"ስምንት አመት....አምስቱን አመት ግን በማሳጅ ስራ ላይ ነበር ያሳለፍኩት ከዛ እሱን ተውኩና የሴኩሪቲና የሹፍርና ስራዎችን ወደመስራት ቀየርኩ።››
ይሄንን ስትሰማ ይበልጥ ተነቃቃች።"ቆይ ቆይ አንተ ማሳጅ ትሰራ ነበር?"
መልሱን ከመመለሱ በፊት ከመቀመጫው ተነሳና ወደፍሪጅ በመሄድ ተጨማሪ ቢራ በማምጣት ለሁለቱም ተጨማሪ ከፈተና ቁጭ አለ።
"አዎ እርግጥ ወታደር ቤት እያለሁ የተወሰነ የወጌሻ ስራ እሰራ ነበር..ትንሽ ስልጠናም ወስጄ ነበር። ከወታደር ቤት ተቀንሼ ስራ ፈትቼ ስንገላወድ ይሄን ስራ አገኘሁ..ተጨማሪ ስልጠና ተሠጠኝና ስራውን ጀመርኩ…በጥቂት ወራት ውስጥ ዝነኛ ባለሞያ ሆንኩ።

"ይገርማል...ስራው ግን እንዴት ነበር...?አስደሳች ነው? ይከብዳል? እስኪ  በፈጣሪ የሆነ ነገር ንገረኝ? "ፈጣን መልስ ብትጠብቅም እሱ ግን ፊቱን በማጨለም አቀረቀረ...››
"ምነው?"
"እኔ እንጃ ምን እንደምልሽ አላውቅም...አንቺ ገና ወደስራው ልትገቢ ስለሆነ የምናገረው ነገር አላስፈላጊ የሆነ አሉታዊም ሆነ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንዲያሳድርብሽ አልፈልግም፡፡"
"ኖኖ...እኔ እኮ የነገርከኝን ሁሉ እንዳለ ተቀብዬ በቀላሉ የምሸማቀቅ ወይም የምፈነድቅ ህፃን አይደለሁም። እኔ አጠቃላይ ግንዛቤ እንዲኖረኝ ስለምፈልግ ብቻ ነው የምጠይቅህ"
"እንግዲያው ስራው ከላይ ስታይው ማራኪ፤የሠው ልጅን ከጭንቀቱ የምንፈውስበት፤ ከተዛባ የሠውነት መዋቅሩ የምናስተካከልበት፤አካሉን፤ አእምሮና ነፍስን በአንድ ላይ እንዲዘምሩ የሚደረግበት ነው፡፡ እና ምንድነው ችግሩ?››
"ችግሩ ይሄንን ጉዳይ ከአንቺ ጋር አንስቼ በግልፅ በመነጋገሬ ትብለጥም ሆነች ሰገን ደስተኛ አይሆኑብኝም"
"ምነው ካሜራ ቤትህ ውስጥ ቀብረዋል እንዴ"
"አይ እንደዛ አይነት ነገር እንኳን የለም"
"ታዲያ ይሄ እኮ በእኔና  አንተ  መ ካከል  የሚቀር  ጫወታ ነው፡፡ አሁን  ምንም ስለ ስራው መጥፎነትና አስቸጋሪነት ብትነግረኝ ወደኃላ የምልበት ጊዜ  ላይ.አይደለም.ያለሁት....ወደድኩም ጠላሁም ወደፊት መጓዝ አለብኝ...ደግሞም

ጓደኛሞች ሆንን አይደል" ብዙ ዝርዝር ነገሮችን በመዘርዘር የልቡን  እውነት ሳይደብቃት ግልፅ ሆኖ እንዲነግራት ልታሳምነው ሞከረች፡፡
‹‹ምን  መሰለሽ... እኛ  ጋር የሚሰራው ማሳጅ ከኖርማሉ  ትንሽ  ለየት   ያለ ወይም በተወሰነ መንገድ ያፈነገጠ..ህግ ወይም ገደብ የሌለበት ልቅ ነው። በቀላሉ እንዲገባሽ ኖርማሉ ማሳጅ ሲጋራ ማጨስ ቢሆን እኛ ጋር ያለው ግን.በሲጋራው ፓኮ ሲጋራ መስሎ የተጠቀለለ ሀሺሽ መሳብ በይው...››
ንግግሩ  በውስጧ የነበረውን የከራረመ ስጋት ቀሰቀሰባት...፡፡
"ግን ይገኝበታል ያሉት ገቢ ይገኝበታል..?እውነት ነው?"
‹‹በዛ ጥርጣሬ አይግባሽ...እኔ በጣም አጥፊ የምባል ሰው ነኝ፤ግን ደግሞ አንድ የስራ ቱርቦ ገልባጭና፤ይሄንን ቤት የገዛሁት በዚህ ስራ ነው።"
በሰማችው ነገር ደስታ ተሠማት ፤ለአባቷ  ዘመናዊ  እና  ምቹ  መራመጃ አርቴፊሻል እግር ስታሰራለትና እንደልብ ከቦታ ቦታና ከዛም አልፎ     ከሀገር ሀገር የሚንቀሳቀስበት መኪና ስትገዛት በምናቧ ሳለችና በውስጧ ደስታ ተጥለቀለቀባት፡፡እርግጠኛ ወደመሆኑ መጣች።አዎ ለዛ ደግሞ  ቀሪ  ህይወቷን በክፍያ መልክ ማቅረብ ቢገባትም ያለቅሬታ ለማድረግ ወስናለች።
"በረሀብ ገደልኩሽ አይደል...እዚህ ቅርብ አንድ ሆቴል አለ…ወጣ ብለን ምግብ እንብላ፡፡"
ግራ ተጋባች፡ ቤቱ ሲያመጣት ለደቂቃዎች ቆይታ ልብስ እስክቀይር ድረስ ብቻ ብሎ ነው። እሷም እንደዛ አምና ነበር ተከትላ ቤቱ የገባችው፡፡ አሁን  ከአንድ ሰዓት በኋላ እንንቀሳቀስ ሲላት ልክ ለማደር እንደመጣ ሰው ድንግርግር አላት፡፡


💫ይቀጥላል💫

ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube 

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍68🥰32👏1
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ


#ክፍል_ሀያ_አንድ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


"ውይ ለመክሰስ ሆቴል...?ሰርቼ ልጋብዝሽ የምትለኝ መስሎኝ ነበር።"
‹‹ደስ ይለኝ ነበር...ግን ካገዝሽኝ ነው..."

"ይቻላል"
ሁለቱም  የየራሳቸውን  ቢራ  ይዘው  በእሱ  መሪነት  ወደ  ኪችን.አመሩ።
ኪችኑ በእጅጉ የተደራጀና የሚያምር ነው። ፍሪጁን ከፈተና ተመለከተ...
"ምን እንስራ"በራሱ መወሰን አቅቶት ጠየቃት።
"እኔ እንጃ...ምን አለህ?"አለችና ወደእሱ ተጠግታ ያለውን ነገር ተመለከተች...ብዙ ምርጫ አላቸው...የምትፈልገውን ነገር እየመረጠች ከፍሪጁ ማውጣት ጀመረች፡፡ እሱም ወደውጭ ሊወጣ አስቦ የለበሰውን ጃኬት አወለቀና ሽርጥ ለበሰ..ለእሷም ተመሳሳይ ሽርጥ ሰጣት።በ30 ደቂቃ ውስጥ ሶስት የተለያየ የምግብ አይነት ተጋግዘው በመስራት ሳሎን የምግብ ጠረጴዛ  ላይ  አቀረቡ..በልተው  ሲጨርሱ አንድ ሰዓት አልፎ ነበር።

"አሁን በላሁ ጠጣሁ...ወደማድርበት ቤርጎዬ ልትመልሰኝ ትችላለህ?›› አለችው። ሞባይሉን በማውጣት ሰዓቱን አየና"እንዴ ገና አንድ ሰዓት  እኮ  ነው...ባይሆን አንድ ወዳጄ ከፈረንሳይ ያመጣልኝ ልዩ ወይን አለኝ...እሱን ላምጣና መጠጥ እንቀይር››አለና እሺታዋንም ሳይጠብቅ መቀመጫውን ለቆ ወደመኝታ ቤቱ በመሄድ ይዞ መጣና የቢራ ጠርሙሶችን ከፊታቸው በማንሳት በወይን ብርጭቆ ተካውና ተደላድሎ ቁጭ አለ፡፡:

"በቀደም  ለታ  ግን  ማደሪያ  ቦታ  ስጠይቅህ  ለምን  ቤትህን  አራተኛ  ምርጫ አድርገህ አላቀረብክልኝም ነበር?"ስትል.ያላሰበውን ድንገተኛ ጥያቄ ጠየቀችው።
"እኔ  እንጃ...ምን  አልባት  እንደዛ  ብልሽ  ሌላ  ነገር  ታስቢያለሽ  ብዬ.ፈርቼ ይሆናል"አላት፡፡
"እንዴት ሌላ ነገር አስባለሁ?"
"ብታስቢም እኮ አይፈረድብሽም...በጥልቀት አታውቂኝም"
"ለነገሩ እውነትህን ነው፤እሺ አሁን ብዙ ብር ከምትዝቅበት የማሳጅ ስራ ራስህን ለምን እንዳገለልክ ንገረኝ? "ቅድም ጀምረው ወዳቋረጡት የጫወታ ርእስ መለሰችው፡፡
የወይኑን ብርጭቆ አነሳና ውስጡ ያለውን ከጨለጠ በኃላ መልሶ አስቀምጦ አንገቱን አቀረቀረ፡፡››
"ምነው ከባድ ጥያቄ ነው እንዴ የጠየኩህ?" በረጅሙ ተነፈሰ፡፡
"ከከባድም በላይ..አየሽ ቅድም ስለስራው ሳስረዳሽ ልክ እንደሀሺሽ ነው ብዬሽ ነበር አይደል። በመጀመሪያ ሁሉ ነገር አስደሳችና ልብን ስውር የሚያደርግ ነበር። አገልግሎቱን ለማግኘት የሚመጡት ሴቶች ሊነኳቸው የሚያሳሱ  የሰውነታቸው ቆዳ እንደሀር ጨርቅ የለሠለሠ፤ የፊታቸው ውበት የመላእክት የመሰለ ፤ጠረናቸው ጭንቅላት አዙሮ ጭናቸው ስር የመድፋት ኃይል ያለው፤ የህልም አለም ንግስቶች ናቸው። ታዲያ እነሱን እርቃን አስወልቀሽ ከላይ ከጭንቅላታቸው እስከታች የእግር ጥፍራቸው መላ ሰውነታቸውን አፍተልትለሽ ዳብሰሽና አሽተሽ፤በስሜት ሲወራጩና በደስታ እንባቸው ሲንጠባጠብ አይተሽ...ለምነውና በአይናቸው ተለማምጠው እርቃንሽን ከእርቃናቸው እንድታዋህጂ ለምነውሽ...አርክተሻቸውና.ረክተሽ፤አስደስተውሽና ተደስተሽ፤ አስለቅሰሻቸውና አልቅሰሽ  ከዛ  ደግሞ  ረብጣ ብር የእጅሽ መዳፍ ላይ አስጨብጠው..በመፍለቅለቅ ጉንጭሽን ወይም ከንፈርሽን ስመው በሳምንቱ እንደሚመለሱ ምለውና ተገዝተው ይሄዳሉ...;
‹‹ስራው እስከዚህ ይሄዳል ማለት ነው"

"አዎ ምነው የፈረምሽውን ውል በቅጡ አላነበብሽውም እንዴ...ደንበኛ ምንም ነገር ጠይቆ መከልከል የለበትም ይላል እኮ.ያ ማለት ደግሞ ስራው ከነገርኩሽም በላይ ይሄዳል ማለት ነው.."
"እና አሁን አንድ የማላውቀው ሰው መጥቶ እንድትወጪልኝ እፈልጋለሁ  ካለኝ..ዝም ብዬ እከፍትለታለሁ ማለት ነው።"

‹‹አይ ዝም ብለሽማ አትከፍቺለትም ...አንቺ ያለሽበት ቦታ አገልግሎትሽን ፈልጎ የሚመጣው ግለሰብ በየሄደበት ዝም ብለው የሚከፍቱለት ቁጥር ስፍር የሌላቸው አንዳንዴም ካንቺ በላይ ለጋ፤ ካንቺ በላይ ፀሀይ የመሰሉ ውብ የሆኑ ሴቶች አሉት...እንደዛ ካደረግሽ ደብሮት የመጣውን ሰውዬ ጭራሽ አሳብደሽ ነው የምትልኪው››

‹‹እና ምንድነው ማድረግ የሚጠበቅብኝ ?››በከፍተኛ መገረም ጠየቀችው።
እጅሽ ሰውነቱ ላይ ሲያርፍ ልስላሴውና ሙቀቱ ቆዳውን ሳይሆን ልቡ ላይ ሊሰማው ያስፈልጋል....መሳም ኖሮብሽ ከሳምሽው ከከንፈሮችሽ የሚመነጨው ሙቀት ወደ ጭንቅላቱ ሄዶ በቢሊዬን የሚቆጠሩትን የኒሮን ሴሎችን ከተኙበት መቀስቀስና መደነስ እንዲችሉ ማድረግ አለብሽ... ልብሶችሽን  ፊቱ  ስታወልቂ አይኖቹ ቆዳሽን ሰንጥቀው ውስጥሽ በመግባት ነፍስሽን ጭምር ለመቆረጣጠም እስኪመኝ መቃተት መቻል  አለበት። ጭንሽን  ከፍተሽለት  ብልቱ ብልትሽን ሰንጥቆ ከገባ አካሉ መጥፋት፤አእምሮ መሰወር፤ነፍሱ በአየር ላይ እየተንሳፈፈች ትዕይንቱን መታዘብ አለባት።ሰውዬው ካንቺ በፊት ከመቶ ሴቶች ጋር ለአንድ ሺኛ ጊዜ ወሲብ አድርጎ የሚያውቅ ከሆነ .. እንዴ ከዚህ በፊት ወሲብ አድርጌ አውቅ ነበር እንዴ ..?ብሎ እስኪጠይቅና እስኪወነባበድ ድረስ ህልም ውስጥ እንዲገባ ማድረግ ይጠበቅብሻል... የስራው ከባድነት ደግሞ ሰውዬው በሳምንት ወይም በወራት ልዩነት ደጋግሞ ቢመጣ በተመሳሳይ ብቃት ግን ደግሞ ፍፁም ባልተደጋገመ 10 የተለያየ መንገድ ማስተናገድ ይጠበቅብሻል፡፡
"የሚያወራውን ሁሉ የምታዳምጠው ሁሉንም የስሜት ህዋሳቶቿን ከፋፍታ ነበር...እየጠጣችው ያለው መጠጥ እየሠማችው ካለው ወሬ ጋር ተዳምሮ ሙቀትና ንዝረት ለቀቀባት
"የምትነግረኝ ነገር ሁሉ ግን እውነት ነው?ማለቴ እንደዚህ አይነት ነገር አለ?"
"አዎ አለ"
"ወይ በፈጣሪ..ታዲያ እኔ ምን  ላደርግ  ነው?  እንደው  ፍቃደኛ  ሆኜ የተጠየቅኩትን ለማድረግ ፈለኩ ልበል…ግን በየትኛው ብቃቴ ነው አንተ ባወራህልኝ መጠን በአየር ላይ የሚያንሳፍፍ ወሲብ መፈፀም የምችለው..?
"አይዞሽ ...አንቺ ብቻ ከልብሽ ተቀባይ ሁኚ እንጂ…በቂ ስልጠና ይሰጥሻል...ከዛ የተወሰነ የስራ ልምድ በኋላ እርግጠኛ ነኝ ከነገርኩሽም በላይ የተካንሽ ትሆኚያለሽ"
"እንዴት እርግጠኛ ሆንክ?"ብላ ልትጠይቀው ፈለገችና ብዙ በተናገረች  ቁጥር ይበልጥ ራሷን እያጋለጠችና ወደ ሽብር ውስጥ እየገባች ስለመጣች መልሳ ዋጠችው።
"እሺ ይሄን ለጊዜው ተውና ..የጀመርክልኝን የራስህን ታሪክ ቀጥልልኝ"
"አጠር ላድርገውና በተደጋጋሚ ጊዜ ከሚመላለሱ ደንበኞቼ መካከል ከአንዷ ጋር የተለየ ግንኙነት ነበረኝ፣ለነገሩ ከአንዷ ጋር ብቻ አልነበረም ከአምስት ከስድስቱ ጋር በይው። ግን ስራ እንዳቆም ስላስገደደቺኝ አንዷ ብቻ ላውራሽ።
የባለስልጣን ሚስት ነች። ባሏ የሆነ መስሪያ ቤት ሚኒስትር ዲኤታ ነው። ያው በስራውም በራሱ ጉዳይም በጣም እረፍት የሌለው ከወር ውስጥ ግማሹን ቤቱ
የማያድር...በሚያድርባቸው ጥቂት ቀናትም እኩለ ለሊት ገብቶ ወፍ ሲንጫጫ የሚወጣ አይነት አባወራ ነው። ሚስቱ የፈለገችውን ያህል ብር ይሰጣታል። በዛ ላይ በእሷ ስም የተከፈተ ግዙፍ ድርጅት አላቸው። የት ገባህ የት   ወጣህ እንዳትለው ያንን በማስተዳደር ቢዚ ሊያደርጋት ሞክሮ ነበር። ይሄ  እቅድ ለተወሰነ አመት ቢሰራለትም ቀስ በቀስ ሴትዬዋን ለድብርትና   ለጭንቀት እያጋለጣት መጣ ...ከዛ በአንድ ወዳጇ ገፋፊነት እኛ ጋር ትመጣለች..አጋጣሚ ሆኖ እኔ ጋር ተላከች። በመጀመሪያዎቹ ሶስት አራት   ዙሮች እንደማንኛውም ኖርማል  ማሳጅ  የተለመደውን  አገልግሎት  እያገኘች   ነበር የምትሄደው...ከዛ ነገሮች በሂደት እድገት ሲያሳዩ ከስድስት ወር የደንበኝነት መመላለስ በኃላ ጥልቅ የሆነ ፍቅር ውስጥ ገባች...
👍68😱54
እውነቱን ለመናገር እኔም ለእሷ የተለየ ስሜት ነበረኝ። እኔ የምትፈልገውን ፍቅርና ወሲብ ስሰጣት እሷ ከጠየኳት በላይ ብር ስትሰጠኝ...ምንም ሳይፈጠር ከሁለት አመት በላይ አሳለፍን... ከዛ አረገዘች።
"ከማ ካንተ?"
"ቆይ ልነግርሽ አይደል...ያረገዘችው ከባሏ ነው፡፡ማለት  በወቅቱ  ሁለታችንም እንደዛ ነው ያሰብነው። ሆዷ እየገፋ ሲሄድ ለማሳጅ ብላ መምጣት ብታቆምም ግን እየተደዋወልን እንደ አመቺነቱ እኔ  ቤትም  ሆቴልም  እንገናኝ  ነበር..ይገርምሻል ይሄን ቤት ስገዛ 2 ሚሊዬን ብር ጎሎኝ እሷ ነበረች የሞላችልኝ፡
የስምንት ወር  እርጉዝ  እያለች  ባሏ  ይዞት  አሜሪካ  ሄደና  እዛ  ጥሏት መጣ…ለምን እዛ የወሰዳት ይመስልሻል፡፡ ከእሱ አብራክ ወጥቶ የሚወለደው ልጅ አሜሪካዊ እንዲሆን ሂሳብ ሰርቶ ነው፡፡ አየሽ ባለስልጣኖቻችን የሚያስተዳድሯትን ሀገር እንዴት እንደሚንቋት፤ሀገራችውን.በሀቅና  በእውነት  አገልግለው ከማበልፀግ ይልቅ ልጆቻቸውን የበለፀገ ሀገር ዜጋ ስለማድረግ ነው ቀንና ሌሊት የሚጨነቁት፡፡ ለማንኛውም ልጅቷ ከሄደች በኃላ በስልክና በኢሜል መገናኘት ቀጠልን…ከዛ መውለዷን አበሰረችኝ… ለዛውም ሁለት መንታ ሴቶች፡፡ ከዛ በኋላ ቀስ በቀስ ግንኙነቴን እየቀነስኩ መጣሁ፤ ስትደውልልኝ አይቼ እንዳላየ  መሆን ሶስት አራቱን አልፌ በአምስተኛው ማንሳት….ግን ምን ያደርጋል ከወለደች ከሶስት ወር በኋላ ባሏ ይዟቸው ሊመጣ ተመልሶ ወደአሜሪካ ሄደ…ግን ሊመለሱ ባሉበት ወቅት የልጆቹን አባት ማንነት የሚያረጋገጥ መረጃ ተፈለገና ዲ.ኤን. ኤ ተሰራ ፡
‹‹የእኔ ልጆች ሆኑ እንዳትለኝ?›አለችው ሳባ በጉጉት፡፡
‹‹አንዱ  ልጅ የባለቤቷ…  ሌላኛው ደገሞ   የሌላ ሰው ሆኖ ተገኘ፡፡››
‹‹እንዴት ሆኖ….?እንደዛ  አይነት  ነገር  አለ  እንዴ…?ማለቴ  አንድ  ሴት  በአንድ ጊዜ ከሁለት ወንዶች ማርገዝ ትችላለች እንዴ?
‹‹እኔም ይሄንን ነገር እስክሰማ እንደእዛ  አይነት ክስተት  እንዳለ አላውቅም ነበር….ወላጆቹም እንደዛው መጀመሪያ ውጤቱን ሲቀበሉ የሆነ የማሽን ስህተት አድርገው በእርግጠኛነት እንዲደገም አደረጉ….የተለወጠ ነገር አልነበረም..ይሄንን በስልክ ስትነግረኝ የምለውን ነበር ያጣሁት….እሷ ልጁ የእሱ ካልሆነ የእኔ እንደሆነ እርግጠኛ እንደሆነች ደጋግማ ነገረቺኝ…እኔም አመንኳትና ተመልሳ መጥታ ልጄ እስከማውቀው በጉጉት መጠበቅ  ጀመርኩ…በዚህ ምክንያት ባሏ ከፈታትም እኔ ሳላቅማማ እንደማገባት ደጋግሜ ነገርኳት….ከእሷ ለመራቅ አደርግ የነበረውን  ጥረት  ሁሉ  እርግፍ  አድርጌ በመተው እስክትደውልልኝ ሁሉ መታገስ አቅቶኝ እኔው ራሴ እደውልላት ጀመር….እና ወደሀገር ተመልሳ መጥታ ባሏን  ፈታ ታገባኛለች  የልጅ አባት ታደርገኛለች በሚል ጉጉት ከመሄዷ በፊት በእሷም ገንዘብ እርዳታ ጭምር ገዝቼ የነበረውን ይሄን ቤት በእቃ ሞላሁት…. ..ይመጥናታል ወይም ያስደስታታል የልኩት አንድም ነገር አልቀረኝ….ደብተሬ ላይ ያለውን ብር ጨርሼ ብድር እስክገባ ድረስ….
ግን ድንገት ስልኳ ጠፋብኝ፤ኢሜልም ብልክላት መልስ የለም.በፌስቡኳም በቀን እስከመቶ ጊዜ መልዕክት ብልክላት መልስ ከየት ይምጣ….


💫ይቀጥላል💫

ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube 

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
54👍38
አትሮኖስ pinned «#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ ፡ ፡ #ክፍል_ሀያ_አንድ ፡ ፡ #በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ "ውይ ለመክሰስ ሆቴል...?ሰርቼ ልጋብዝሽ የምትለኝ መስሎኝ ነበር።" ‹‹ደስ ይለኝ ነበር...ግን ካገዝሽኝ ነው..." "ይቻላል" ሁለቱም  የየራሳቸውን  ቢራ  ይዘው  በእሱ  መሪነት  ወደ  ኪችን.አመሩ። ኪችኑ በእጅጉ የተደራጀና የሚያምር ነው። ፍሪጁን ከፈተና ተመለከተ... "ምን እንስራ"በራሱ መወሰን አቅቶት ጠየቃት። "እኔ…»
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ


#ክፍል_ሀያ_ሁለት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


ሳምንት ሙሉ ታገስኩ….ላብድ ደረስኩ…ስራ ሁሉ መስራት አቃተኝ….ከ15ቀን  በኋላ ሰውዬውን የሆነ ስብሰባ ሲመራ በቲቪ አየሁት….ደስ አለኝ፡፡ልክ እሷን ያገኘሁ ነው የመሰለኝ…..በቃ እሷም መጥታለች ማለት ነው ስል አሰብኩ….ማንንም እንዳታገኝ ቤት ውስጥ ቆልፎባታል ስል በማሰብ እርግጠኛ ወደመሆን ተሸጋገርኩ እሷን ነፃ ለማውጣት ወሰንኩ፡፡ ጓደኞቼን እንዲረዱኝ ጠየቅኩ፡፡ የሰውየውን ቤት ቀንና ሌሊት ማጥናትና መሰለል ጀመርን፤የሚገባውንና የሚወጣውን ሁሉ መከታተል ቀጠልን…በአራተኛው ቀን ቤቱ ያሉት አንድ የቤት ሰራተኛ አንድ ነርስ እና አንድ ህፃን ልጅ ብቻ እንደሆኑ አረጋገጥን›› የምሆነውም የማደርገውም ነገር ግራ ገባኝ…ሰራተኛዋ እቃ ለመግዛት ከቤት ስትወጣ ጠብቀን አገትናትና አስፈራርተን መረጃ ጠየቅናት..ሴትዬዋም ፈርታ  ስለነበረ የምታውቀውን ሁሉ ምንም ሳታስቀር ዘረዘረችልን፡፡

‹‹ምን አለቻችሁ ?ምን ሆና ነው?››ሳባ የተፈጠረውን ለማወቅ በጉጉት ጠየቀች፡፡

‹‹ሚስቱ ከአሜሪካ ወደሀገሬ አልመለስም ብላ አንደኛውን ልጅ ይዛበት እንደተሰወረች..ለ15 ቀን ከዛሬ ነገ ተመልሳ ትመጣለች ብሎ ሲጠብቃትና ሲያስፈልጋትም ከቆየ በኋላ ተስፋ ቆርጦ የተወችለትን አንደኛውን ልጁን ይዞ ወደ ሀገር እንደተመለሰ እንደነገራቸው፣…እና ሁልጊዜ ወደቤት ሲገባ እሱን እያሰበ እንደሚያዝንና እንደሚተክዝ ነገረችን….ላምን አልቻልኩም፡፡

በሰማሁት ዜና በጣም ተረበሽኩ..ላብድ ደረስኩ‹‹እሷ በፍፁም እንደዛ አታደርግም..አንደዛ ብታደርግ ኖሮ ቢያንስ ካለችበት ቦታ ለእኔ የሆነ መልዕክት ትልክልኝ ነበር…ኢሜሌንም ሁለቱንም ስልክ ቁጥሬን በቃሏ ልክ እንደገዛ ስሟ ነው የምታውቀው….እና የሆነ ነገር እንደሆነች ገባኝ፡፡ በህይወቴ ወሰንኩና እሷ ምን እንደሆነች ለመረዳት አንድ አደገኛ ነገር ለማድረግ ወሰንኩ በሁለት ቦዲጋርድ እየታጀበ ወደቤቱ የሚመጣውንና የሚሄደውን ሚኒስቴር ዲኤታ በጓደኞቼ እገዛ ቤት ውስጥ ገብቼ በገዛ መኝታ ቤቱ ለመተኛት ሲገባ ጠበቅኩና ሽጉጥ ግንባሩ ላይ ደቅኜ እጆቹንና እግሮቹን ጠፍሬ ከወንበር ጋር አሰርኩትና እውነቱን እንዲነግረኝ ጠየቅኩት››

‹አንተ ነህ ማለት ነው ውሽማዋ?››ሲል ጠየቀኝ፡፡

‹‹ሚስትህን  እንደዛ  አይነት  ስህተት  ውስጥ  እንድትገባ  የገፋፋሀት  አንተው  ነህ
…ምንም አይነት ለአሷ የሚሆን ጊዜ አልነበረህም….››አልኩት፡፡

‹‹እና በእኔ ላይ መሸርሞጧ ትክክል ነው ትላለህ?››

‹‹አንተም እኮ ስፍር ቁጥር ከሌላቸው ሴቶች ጋር በየሆቴሉና ሎጁ ስትቀብጥና ስትሸረሙጥ መኖርህን አውቃለሁ…ከፈለክ መረጃው አለኝ….አልኩና ሞባይሌ ላይ ከነበሩት አንድ ሶስት መረጃዎች ውስጥ ከፈትኩና አሳየሁት›

‹‹እና እኔ ስላደረኩት እሷ ማድረግ አለባት እያልክ ነው…?ደግሞ ቢያንስ እኔ እኮ ልጅ ወልጄ አላመጣሁባትም››

‹‹አይ አንተም ንፁህ አይደለህም ስለዚህ ይቅርታ ይገባታል እያልኩህ  ነው…አሁን የት ነው የቆለፍክባት?››
‹‹የምን መቆለፍ…ጉዷ ተፍረጥርጦ ሲወጣ እዛው  አሜሪካ  ነው  አንደኛውን ልጇን ይዛ የተሰወረችው›› ብሎ ሊያታልለኝ ሞከረ….ብዙ ሞከርኩ ሲያስቸግረኝ አፉን አፈንኩትና ገልብጬ እግሩ እስኪተለተል ወፌ ላላ ስገርፈው…በመጨረሻ አመነልኝ፡፡ ሲጨቃጨቅ ድንገት እንደመታትና እንደሞተችበት…ከዛ ለአሜሪካ ጋንግስተሮቸ ብዙ ብር ከፍሎ እሬሳዋ እንዲወገድ እንዳደረገ እና የእሱ ያልሆነውን ልጁም ነጥሎ ለማደጎ ድርጅቶች እንደሰጠ አፉን ሞልቶ ነገረኝ….ልጁን የሰጠበትን የማደጎ ድርጅት አድራሻ ተቀበልኩትና ልገድለው ፈለኩ፤ከራሴ ጋር ለበርካታ ደቂቃዎች ተሟገትኩ ግን የልጄ ወንድም አባት ነው…እንዴት ምንም ያማያውቀውን ህፃን ያለእናት መቅረቱ ሳያንስ ያለአባት አስቀረዋለሁ? ብዬ አሰብኩ….፡፡

ከዛ ስለእኔ ለሌላ ሰው ቢያወራ ሊበቀለኝ ሙከራ ቢያደርግ እሱንም አሳልፌ እንደምሰጠው ስልጣኑንም ክብሩንም አጥተን እስር ቤት እንዲበሰብስ እንደማደርገው ነግሬ በገባሁበት ቦታ ጋርዶቹ ሳያዩኝ ጥዬው ወጣሁ፡፡
‹‹እና አላሳሰርከውም?››
‹‹ባሳስረው ምን ይጠቅመኛል…?አራስ ልጅ እኮ አለው...ልጁ ደግሞ ምንም ቢሆን የእሷ ነው››
‹‹ከዛ በኋላ ሊያጠቃህ አልሞከረም?››
‹‹በፍፁም ስሬ ድርሽ አላለም፡፡››
‹‹እና ልጅህን የምታስመልስበት ምንም መንገድ አላገኘህም?.››
አሜሪካ  በሚገኙ  ወዳጆቼ  አማካይነት  ለረጅም  ጊዜ  ካፈላለኩ  በኃላ  የዛሬ  ወር አካባቢ ትክክለኛ አድርሻውን አገኘሁ፡፡››
‹‹በእውነት ደስ ሲል..››
‹አዎ ደስ ይላል.. እሱ ለማደጎ ድርጅት ቢያስረክበውም .ማደጎ ድርጅቱ  ደግሞ አሳዳጊ አግኝቶ ለአንድ አሜሪካዊ ጥንዶች አስተላልፈው ስለሰጡት አሁን በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ማወቅ ችያለሁ…..እግዜር ካለ በቅርብ ሄጄ እንደማየውና ከተቻለ ይዤው እንደምመጣ ከልሆነ እንኳን ከወላጆቹ ጋር  ተዋውቄ  ልጄንም አይቼ መምጣት ፈልጋለሁ..፡፡
‹‹በጣም ነው የማዝነው ሰው ሁሉ ለካ የራሱን ቁስል ይዞ ነው የሚዞረው››ስትል አሰበች፡፡
አዎ..ይሄንን ታሪክ የሚያውቁ በጣም የቅርቤ የሆኑ ጥቂት ሰዎች ናቸው..እና ከዛ በኋላ የማሳጅ ስራ እንዴት መስራት እችላለሁ...? ገና የማሳጅ ጠረጴዛው ላይ የሆነ ሴት መጥታ ስትተኛ ፊቴ ድቅን የምትለው እሷ ነች…..ልክ በገዛ እጄ አንቄ እንደገደልኳት ወይም በገመድ አንጠልጥዬ ነፍሷን እንደነጠቅኳት ይታሰበኝና እጄ ሆነ መላ ሰውነቴ ይንቀጠቀጣል…ከዛ አቃተኝና ይብቃኝ አልኩ…ትብለጥም ከመጀመሪያው ጀምሮ ታሪኩን ታውቅ ስለነበረ ወዲያው ጥያቄዬን ተቀበለችና ይሄንን አሁን የምሰራውን ስራ እንድሰራና ድርጅቱን ልክ እንደቤተሰብ ድርጅት እንዳገለግል ጠየቀችኝ ..እኔም ተቀበልኳት…እና ይሄው ሁለት አመት ድርጅቱ በሚፈልገኝ በማንኛውም ቦታ እየገባሁ ያለውን ስራ ሁሉ እሰራለሁ…በጣም ጥሩ የሚባል ደሞዝም ይከፈለኛል…እና ታሪኩ እንደዛ ነው እልሻለሁ ፡፡
‹‹በጣም ያሳዘናል፡፡››…አለች የእውነትም ከልቧ አዝና…ከመጠጡ ጋር ወደ ውስጧ ያስገባችው አሳዛኝ ታሪክ በሰውነቷ ሙቀት ለቀቀባት…ስትቁነጠነጥ አየና‹‹ ምነው ምን ፈለግሽ?››ሲል ጠየቃት፡

‹‹እኔ እንጃ… ሞቀኝ …ሰውነቴን ለቅለቅ ብል ደስ ይለኛል፡፡››አለችው፡፡

የጠበቀው‹‹መሸ ወደ ሆቴሌ አድርሰኝ›› የምትለው ነበር የመሰለው፡፡ቶሎ ብሎ ተነሳና‹‹ተነሽ ምን ችግር አለው..እንደቤትሸ ቁጠሪው››አለና እየመራ ወደ ውስጠኛው ክፍል ይዟት ሄደ…አንዱን ክፍል ከፍቶ ገባ ተከተለችው፡፡መኝታ  ክፍሉ ከሳሎኑ ብዙም የማይተናነስ ሰፊ ክፍል ነው፡፡መሀከል ላይ ነጭ  አልጋ  ልብስ በስርዓት የተነጠፈበት ነጭ ግዙፍ አልጋ ይታያል…በአንደኛው  የግድግዳ ሙሉ ቁም ሳጥን የተገጠመለት ነው፡፡
‹‹ይሄ ሁሉ ቁም ሳጥን ልብስ ካለበት ይገርመኛል››አለች፡፡
ወደ ቁም ሳጥኑ አመራና አንዱን በራፍ ከፍቶ ከተደረደሩት በርካታ አንሶላና ፎጣዎች ውስጥ አንድ ነጭ ፎጣ አወጣና እያቀበላት
‹‹ያው ግቢና ታጠቢ ሳሎን እጠብቅሻለሁ››አላት፡፡
👍695👎2
‹‹አረ እዚሁ ጠብቀኝ ….መታጠብ እኮ  አይደለም  የምፈለገው  …በሰውነቴ  ላይ ውሀ ማፍሰስና መቀዘቀዝ ነው..››አለችውና ወደ ሻወር ቤት ገባች…ሻወሩ  ምን አልባት እስከዛሬ ካየቻቸው ሻወሮች በጣም ዘመናዊና የሚያምር ሆኖ ነው ያገኘችው…እዚህ ቤት ከገባችበት ሰዓት ጀምሮ ባየችው ነገር በጣም  ቀናች…
‹‹እኔም በቅርብ አመት እነዚህን ሁሉ ይኖሩኝ ይሆን? ››ስትል ነበር በውስጧ የጠየቀችው፤ልብሷን አወለቀችና ገንዳ ውስጥ ገባች….አስር ደቂቃ ብቻ ነው የፈጀባት..ከዛ በሰጣት ፎጣ ሰውነቷን በማደራረቅ ልብሷን መልሳ ለብሳ ወጣች፣አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ ብሎ እሷን እየጠበቃት ነበር….፡፡

‹‹እንዴ ፒጃማ እኮ አዘጋጅቼልሽ ነበር.›አላት የለበሰችውን እየተመለከተ፡፡

‹‹እንዴ እዚህ ነው እንዴ የማድረው?››

‹‹ሰዓቱን አላየሽም አራት ሰዓት እኮ አልፏል…አይዞሽ በደንብ  የተዘጋጀ  የእንግዳ ክፍል አለኝ››አላት

‹‹እንደዛ ከሆነማ ቢጃማውን ብለብስ ይሻላል ››አለችና  የዘረጋላትን  ከእሽጉ ያልተፈታ ቢጃማ ተቀበለችው፡፡
‹‹እንዴ እንግዳ ቤትህ በመጣች ቁጥር እንዲህ አዲስ ፒጃማ ነው እያነሳህ የምትሰጣቸው?››
‹‹አይ .በፍፁም…እኔ እቤቴ እንግዳ አላመጣም….እሷ ብቻ ነበረች የምትመጣው…ለእሷ ብዬ መአት ነበር የገዛሁት፤ግማሹንም ሳትጠቀምበት እንደወጣች በሰው ሀገር አጉል ሆና ቀረች….ሶሪ ወሬዬ ሁሉ ሀዘን በሀዘን ሆነ አይደል?››
‹አረ ችግር የለውም…በቃ ቀይሬ ልምጣ…››
‹‹እዚሁ ቀይሪ እኔ ልውጣልሽ››
‹ችግር የለውም ፊትህን ብቻ አዙርልኝ…››አለችና ዞር ስትል እስከአሁን ያላየችውን ነገር አየች፡፡
‹‹እንዴ ይሄ የማሳጅ ጠረጴዛ አይደል? ››
‹‹አዎ ነው….ያው እንደማስታወሻ በይው፡››
‹‹እና አሁን ማሳጅ ላድርግ ብትል ማድረግ ትችላለህ ማለት ነው?››
‹‹አዎ…ሁሉ ነገር ሙሉ ነው….ቅባቶቹም ጠረጴዛውም.ፎጣዎችም  ትራሶቹም ሁሉ ነገር የተሟላ ነው፡፡አንዳንዴ ቢያስቸግርም  ራሴን  በራሴ  ማሳጅ አደርጋለሁ…እንዴት ነው ለምን ግን ማሳጅ አላደርግሽም…ለእኔም ምን ያህል እንደረሳሁት እራሴን እንድፈትሽ ያግዘኛል››
‹‹መች አሁን?››
‹‹አዎ አሁን ምን ችግር አለው?››
‹‹እሱማ ምንም ችግር የለውም  ››

‹‹እንግዲያው…››ብሎ ተነሳ..ሶስት የሚሆኑ ፎጣዎችን ከቁም ሳጥን  አወጣ…ሌላ ቦታ  አነስ  አነስ  ያሉ የተለዩ ሶስት ትራሶችን አወጣና ወደ.ጠረጴዛው  ወሰደ.ቅባቶችን ካሉበት አወጣና ፊት ለፊት አስቀመጠ
‹‹እንዴ አመረርክ እንዴ?››
ዞር ብሎ አያትና‹‹…እንዴ እስከአሁን አላወለቅሺም?››
‹‹እሺ ላውልቅ ዞር በልልኝ››
‹‹ላሽሽ እኮ  ነው…ማለቴ ሳሽሽ  ሰውነትሽን  እያየሁ.ነው…ለምን ታለፊኛለሽ…››አለና ዞረላት፡፡
ሰውነቷ  በፍርሀት  እየተንቀጠቀጠ  ልብሷን  መልሳ  አወላለቀች፡…በፓንት  ብቻ ወደእሱ ቀረበች.
‹‹ይሄው አወለቅኩ..››ዞር አለና  እርቃኗ  ላይ  አይኑን  ተከለ..  በቀላሉ   ሊነቅል አልቻለም
..‹‹እንዴ ምነው ፓንቴንማ  አላወልቅም››አለችው፡፡

‹‹መች አውልቂ  አልኩሽ…? ነይ ተኚ፡፡›› አላት…ፈጠን  ብላ ሄደችና  ወጣች…በደረቷ ተኛች..አንዱን ትራስ ግንባሯን ስር ..ሌላውን  ትራስ ታች ቁርጭምጭሚቷ አካባቢ አደረገና አንድትመቻች አደረገ….ከዛ ከአልጋ ራስጌ አካባቢ ወዳለው ግዙፍ ጂፓስ ሄደና ለስለስ ያለ ካንትሪ እንግሊዘኛ ሙዚቃ በተመጠነ ድምፅ ከፈተና.. ወደእሷ ተመለሰ፡፡ እጁን  በቅባት  እያራሰ  ቀስ  ብሎ አንገቷ አካባቢ አሳረፈ…ከፍራቻዋ የተነሳ ሽምቅቅ አለች..ቀስ  ብሎ  በሁለት እጆቹ ከአንገቷ ወደትከሻዋ፤ወደ ወገቧ እየወረደ ሲመጣ ቀስ በቀስ ዘና እያለች ሰውነቷ እየተፍታታና መንፈሷም ወደ ጆሮዋ ሰርጎ ከሚገባው  ሙዚቃ  ጋር ተዳምሮ መንፈሷ ዘና  ማለት ጀመረ….ከዛ  ዘለለና  ወደ  እግሯ ጣቶች ሄደ…ውስጥ እግሯን የሆነ የሆነ ቦታዎች ጠቅ ጠቅ እያደረግ ሲነካካት ላይ ጭንቅላቷ ላይ ቀለማት ሲፈነጣጠቁ ተሰማት….ከዛ ከቁርጭምጭሚቷ ተነስቶ ወደባቷ በመውጣት በእግሯ መካከል እስከጥግ እጆቹን እያንሸራሸረ አፈተለተላት..ውስጧ ተተረማመሰ…በቀደም በትብለጥ ትዕዛዝ ማሳጅ ስትደረግ አቅሏን ልትስት ደርሳ ነበር…ያሁኑ ግን ከዛም ላቅ ያለ  ነው..መቀመጫዋ  ላይ ደረሰ…ከነአደረገችው ፓንት ጨመቅ ለቀቅ… ጨመቅ  ለቀቅ  ሲያደርጋት አቃተተች..ከዛ ድንገት ወደመሀከል መጣና ሰቅስቆ  እግሯና  ጀርባዋ  አካባቢ እጆቹን አስገባና ገለበጣት፡፡

ለሰከንድ በተዳከመ እይታ አየችውና መልሳ ጨፈነች፡፡እሱ ስራውን ቀጠለ…..ቅባቱን አነሳና ከላይ ከደረቷ ጀምሮ በሁለት ጡቶቿ ስንጥቅ   አድርጎ ታች እንብርቷ ድረስ ረጨውና እቃውን ወደ ቦታው ወስዶ አስቀመጠ…ከዛ ከእንብርቷ ዙርያ ጀምሮ እላይ ጡቶቿ ዙሪያ እስከአንገቷ ወደታች.እስከቁርጭምጭሚቷ.ሲያፍተለትላት እቅሏን ወደመሳት ተቃረበች….ቀስ ብሎ ፓንቷን ወደታች ስቦ ሲያወልቀው እንኳን ከመተባበር ውጭ አንድም ተቃውሞ አላሰማችም፡፡ከዛ ቅባቱን አነሳና ብልቷ ዙሪያ ታች ባቷን ጭምር አንጠባጠበው…ቅባቱ ወደ ብልቷ ከንፈር አካባቢ ሲንከባለል…ልቧ ተንቀጠቀጠባት…

ደምሳሽ ድንገት እጁን ከአካሏ አነሳና…ወደ ጠረጴዛው ጎንበስ በማለት የሆነ ፔዳል ነገር በእግሮቹ ተጫነ..ከዛ  ጫፋቸው ላይ ሰንሰለት የተንጠለጠለባቸው አራት ብረቶች ከጠረጴዛው ኮርነር እየተሸለቀቁ ወደጎን እየተመዘዙ ወጡ.. ከዛ እጀታቸው ወደላይ ተነሳ…፣እጁን ከሰውነቷ ላይ አንስቶ ሲቆይ…ጨረስኩ ሊላት መስሏት በቅሬታ‹‹…በቃ እንዴ ልነሳ?›› አለችው

‹‹ቆይ ትንሽ ታገሺኝ›››አላት…ና ቀኝ እጇን አንስቶ ሰንሰለቱን ሳበና አሰራት…ግራ ቀኝ እጆቿንም እንደዛ አደረገ..›ግራ ገባት..አይኖቿን ገልጣ

አየችው...ፈራች …በጣም ፈራች…. ቢሆንም ምንም አላለችውም…ይባሰ ብሎ ወደ እግሮቿ ሄደና በተመሳሳይ መንገድ በግራና በቀኝ አሰራቸው

ከዛ ፔዳሉን ረገጥ እረገጥ  ሲያደርገው….መስቀል  ላይ  እንደተቸነከረ  ወንጀላኛ አጆቿ ቀጥታ ሲወጣጠሩ እግሮቿ ደግሞ  ተከፋፈቱ..ከዛ  ቅባቱን  እንደአዲስ በሰውነቷ አዳረሰና .ምንም ቦታ ሳያስቀር እያፍተለተለ ያሻት  ጀመር …አሁን ማጓራት ጀምራለች…….እሱ ግን ቀጥሏል፤

ፔዳሉን ደጋግሞ ሲረግጠው ብረቱ ወደላይ እየተመዘዘ እሷን ከጠረጴዛው አንሰቶ በግማሽ ሜትር ርቀት በአየር ላይ እንድትንጠለጠል አደረጋት
…እንደዛ ሩህ በሚያስት ጡዘት ላይ ሆና ‹‹ወይኔ እየሞትኩ ይሆን እንዴ?››ብላ በማሰብ ላይ ነበረች….ኮመዲኖውን ከፈተና የሚያማምር ቀለም ያለቸው ከተለመደው በጣም ወፍራም የሆኑ ሶስት ልዩ ሻማዎች…ከነማስቀመጫቸው  አወጣና  ለኮሰው…. አንዱን በወገቧ ትክክል ሌላውን መቀመጫዋ አካባቢ ሶስተኛውን ጭኖቾ መካከል፤ከዛ በእጆቹ ሰውነቷ ዙሪያ እየተሸከረከረ ሲያሻት..ከሻማው የሚወጣው ሙቀት ሰውነቷ ላይ ሲሰማትና ቅባቱን እያጋለ ሲያንጠባጥበው….‹‹በፈጠረህ አልቻልኩም. ልሞትብህ ነው….ሞትኩብህ..ልቤን ደከመኝ…ነፍሴ  እየወጣች  ነው….››› መለፍለፍ ጀመረች፡፡.

ሌላውን የሰውነቷን ክፍል ተወና ሙሉ ትኩረቱ ብልቷዋ ላይ አድርጎ ..ከዳር ዳሩ ጀምሮ እያሸ ወደውስጥ ለመግባት እየሞከረ ከዛ ጣቱን እያወጣ እንደአላደገ ቆለጥ ጉንቁል ያለችውን ቂንጥሯን እያፍተለተለ በፈሳሽ እስክትረሰርስ ድረስ   ካስጓራት በኃላ ሻማዎችን አነሳና በፍጥነት ፔዳሉን በተቃራኒው በመጫን   አወረዳትና ጀርባዋ ጠረጴዛው ላይ እንዲያርፍ ከደረገ በኋላ መጀመሪያ ሁለቱን እግሮቿን ከሰንሰለቱ አላቀቀ..
👍725
​​.ከዛ እጆቿን አላቀቀላትና ‹አሁን ጨርሰናል›ሲላት እንደእብድ አደረጋትና ከጠረጴዛው ተነስታ በመስፈንጠር ከንፈሩ ላይ ተጣበቀችበት..ሙሉ በሙሉ ተጠመጠመችበት ከዛም  መሳሟን  ሳታቋርጥ ሙሉ በሙሉ ከእቅፉ ሳትወጣ እሱ የለበሰውን ቲሸርት ከነፓካውቱ ወደላይ መዥርጣ ስታወልቅላት እሱ ደግሞ እንደምንም ታግሎ ቀበቶውን ፈታና ሱሪውን ከነፓንቱ ወደታች አውልቆ ጣለው ..ከዛ ተያይዘው እዛ ውብ አልጋ ላይ ተዘረሩ…ለረጅም ጊዜ ከተገቢው በላይ ስለተሟሟቁ በእኩል ደቂቃ ጡዘት ላይ ለመድረስ አስር ደቂቃ ብቻ ነበር የፈጀባቸው..ከዛ ያ ነጭ ግዙፍና ውድ አልጋ ልብስ በደም ነጠበብጣብ ደመቀ….ብራምባር ተሰበረ..።

💫ይቀጥላል💫

ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube 

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
29👍17🎉1
አትሮኖስ pinned «#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ ፡ ፡ #ክፍል_ሀያ_ሁለት ፡ ፡ #በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ ሳምንት ሙሉ ታገስኩ….ላብድ ደረስኩ…ስራ ሁሉ መስራት አቃተኝ….ከ15ቀን  በኋላ ሰውዬውን የሆነ ስብሰባ ሲመራ በቲቪ አየሁት….ደስ አለኝ፡፡ልክ እሷን ያገኘሁ ነው የመሰለኝ…..በቃ እሷም መጥታለች ማለት ነው ስል አሰብኩ….ማንንም እንዳታገኝ ቤት ውስጥ ቆልፎባታል ስል በማሰብ እርግጠኛ ወደመሆን ተሸጋገርኩ እሷን ነፃ ለማውጣት…»
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ


#ክፍል_ሀያ_ሶስት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ዛሬ ላይ…አሁን

ሳባ ከሰመጠችበት የአመታት ትዝታ ወጥታ…ወዳለችበት ስትመለስ  ከታላቅ መገረም ጋር ነው፡፡በዛን ወቅት በዛን ለሊት በወሲብ የረካችውን እርካታ በህይወቷ ሙሉ ድጋሚ አግኝታው አታውቅም..እናም ደግሞ ፈፅሞ  አትዘነጋውም..እርግጥ ሴት ሆና የመጀመሪያ ቀን የወሲብ ገጠመኟን  በመጥፎም ሆነ በክፉ የማታስታውስ የለችም…የእሷ ግን ከነጣዕምና ከነቃናው ዕድሜ ልኳን ይሄው እንዲህ ስብርብር ብላ አቅሏን  አጥታ ደንዝዛ እንኳን  ምንም የደበዘዘ ነገር የለም፡፡ እንደምንም ከተቀመጠችበት ተነስታ ለመቆም ስትሞክር እግሯ የእሷ መሆኑ እስኪጠፋት ድረስ ደንዝዞ ከቁጥጥሯ ውጭ ሆኗል ..እንደምንም ፈጠን አለችና የበረንዳውን ብረት በመያዝ ቆመች….ከድንዛዜዋ እስክትወጣ ከ5 ደቂቃ በላይ ወስደባት…
ትዝ ይላታል እዚህ ቦታ ስትቀመጥ ከለሊቱ 8 ሰዓት አካባቢ ነበር..አሁን  ግን ነግቶ..ወፎች ግቢ ውስጥ ያሉ ሁለት ዛፎች ላይ ሰፍረው ጭጭጭ እያሉ መንፈስ የሚያንሰፈስፍ ሚስጥራዊ መዝሙር አየዘመሩ ነው…ግቢ ውስጥ ከወዲህ ወዲያ ስትንጎራድድ ዘበኛዋ ለኦሎምፒክ እንደሚዘጋጅ አትሌት በዛ  ለሊት የስፖርት ቱታ ለብሶ ግቢው  ውስጥ  ባለ  ከፍት ቦታ ስፖርት  እየሰራ ነው….በርከት ላሉ ደቂቃዎች ቆማ ተመለከተችው…አንዴ ፑሻፕ ይሰራል፤ደግሞ ክብደት ያነሳል፤ደግሞ ቁጭ ብድግ ይላል፡፡
‹ታድለህ..››አለችና ወደውስጥ ገባች፡፡
…ቀጥታ ወደሻወር ቤት ነው ያመራችው…ሰውነቷን ታጠበች..ለመታጠብ ረጅም ሰዓት ነው የፈጀባት.. ምን አልባትም ከአንድ ሰዓት በላይ....ከዛ ልብሷን ቀየረች..የተወሰነ ሜካፕ በመጠቀም ራሷን አሰማመረችና መድሀኒቷን ወደቦርሳዋ በማስገባት መኝታ ቤቷን ለቃ ለመውጣት ዝግጁ ስትሆን ሁለት ሰዓት ከሩብ ሆኖ ነበር….ቀጥታ ወደሆስፒታል ነው የምትሄደው…እርግጥ ለቀጠሮዋ ሶስት ቀን ይቀረዋል..ግን ደግሞ ላለፉት ሶስት ቀን መድሀኒቷን  አልተጠቀመችም..ያንን ለሀኪሟ ተናግራ መፍትሄ የሚለውን እንዲነግራት ትፈልጋለች….እርግጥ ልታገኘው የፈለገችው ለዚህ ብቻ አይደለም…ከእሱ ጋር መነጋገር ሰላም እንዲሰማት ስለሚያደርጋት ነው፡፡ ፎቅ ላይ ካለው መኝታ ቤቷ ወደሳሎን ስትወርድ ፊት ለፊቷ ባለው የምግብ ጠረጴዛ በምግብ ተሞልቶ አየች…ግራ ገባት…ሞባይሏን አወጣችና ሰዓቷን መልሳ አየችው  2.20 ነው፡፡ተመላላሽ ሰራተኛዋ ከ3 ሰዓት በፊት ስትገባ  አይታት  አታውቅም  …እንደዛ አይነት ንግግርም የላቸውም
‹‹…ታዲያ አንዴት ዛሬ ልታደርገው ቻለች?››በማለት ቦርሳዋን ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠችና ወደኪችን ስትሄድ፤ባዶ ነው፡፡ ኪችኑ ሁሉ ነገር ፅድት ብሎ እቃዎች ሁሉ በየቦታቸው ስለተቀመጡ ከነጋ ሰው የገባበትም አይመስልም፡፡ ቀጥታ ወደምግቡ ተመለሰችና እየጣፈጣት የምትፈልገውን ያህል ከተመገበች በኃላ እጇን ተጣጥባ ቦርሳዋን ይዛ ወጣችና ቀጥታ ወደ መኪናዋ ስትሄድ ትናንት ከአሰላ ስትመጣ አልብሷት የነበረውን አቧራና ጭቃ ከላዩ ላይ ተወግዶ ፏ ብላ ፀድታለች፡፡ደስ አላት፡፡ገባችና ቁልፏን አሽከርክራ ሞተሩን ማሞቅ ጀመረች በዚህን ጊዜ  የመኪናውን ድምፅ ሰምቶ ከዘበኛ ቤት ወጣና በራፉን ከፈተላት..መኪናዋን አንቀሳቀሰችና .ስሩ.ስትደርስ.አቆመች አንገቷን በመስኮት አወጣችና..‹‹መኪናዬን ንፁህ ስላደረክልኝ አመሰግናለሁ››አለችው
‹‹አረ ችግር የለውም…ቁጭ ከምል ብዬ ነው››

‹‹ሳሎን ቁርስ አለልህ.. ግባና ብላ ››

‹‹እሺ እበላለሁ››

‹‹እሺ  ቻው›ብላ መኪናዋን አንቀሳቀሰችና  ወዲያው መልሳ አቆመችው፡፡

‹‹ይቅርታ ስምህ አይያዝልኝም››

‹‹ቀናው››

‹‹ያልተለመደ ስም ነው…ቆይ አለም መጥታ ነበረ አይደል.?ታዲያ.የት ሄደች?››
‹‹መቼ? ዛሬ ከሆነ አልመጣችም፡፡››

‹‹ታዲያ ቁርሱን ማን ነው የሰራው?››አቀረቀረ…

‹‹ምነው መልስ የለህም?››ኮስተርተር ብላ ጠየቀችው፡፡

‹‹ምነው የማይሆን ነገር ሰራሁ እንዴ?››

የምትመልሰው  ግራ  ገባት ‹‹እኔ እንጃ.. ለማንኛውም  በጣም ይጣፍጣል›› አለችውና ከመገረም ውስጥ ሳትወጣ መኪናውን አስነስታ ተፈተለከች፡፡
ከዶክተሩ ጋር ተገናኝታ ፊት ለፊት ተቀምጣለች…የሆነውን ነገር ሁሉ  ነግራው ምክር እየሰጣት ነው፡፡
ይሄውልሽ ሳባ .ይሄንን ነገር ሲሪዬስ አድርገሽ እንድትወስጂው እፈልጋለሁ››
‹‹እሺ ዶ/ር ሁለተኛ አይለመደኝም፡፡››
‹‹ቤተሰቦችሽም ሊረዱሽ ይገባል፡፡››

‹‹ቤተሰቦቼ አሰላ ነው ያሉት‹‹ያንን ማድረግ አይችሉም፡፡››

‹‹ሳባ ከእኔ በተጨማሪ በቅርብሽ ሆኖ ሁሉን ነገር እየተከታተለ ሊረዳሽ   የሚችል ሰው ማግኘት አለብሽ.››.
‹‹አይ ዶ/ር እንዲሁ እድሜ ለመግፋት ካልሆነ በስተቀር የእኔ ነገር ተስፋ.ያለው........ .አይመስለኝም…በአጠቃላይ.መኖርደክሞኛል..መጨረሻ.መዳረሻዬ.
መቃብር ቤት፤
   ከዛ  ካመለጥኩ  በሰንሰለት  ታስሬ  አማኑኤል…በጣም  እድለኛ  ከሆንኩ  ደግሞ እስር ቤት የሚሆን ይመስለኛል››

‹‹ከእንደዚህ አይነት አሉታዊ አስተሳሰቦች ራስሽን ማራቅ አለብሽ..አሉታዊ ሀሳብ ቀስ በቀስ በመጀመሪያ በአዕምሯችን ስሩን እየሰደደ ይሄዳል.. ከዛ የምናስብበትን መንገድ ይቀይራል፡፡ እኛ ደግሞ የሀሳባችን ውጤት ስለሆንን በሂደት በአላስፈላጊ መንገድ እንድንጓዝ እየቀየረን ይሄዳል፡፡ ቀድሞ የማናውቀው አይነት ሰው ከውስጣችን ይበቅላል››

    ‹‹.ይበቅላል አልክ…በቅሎ አድጓል እኮ…ብቻ ዶ/ር ሁሉ ነገር ይጨንቃል››

   እኮ የምልሽ እሱን ነው.መድሀኒቱ ብቻውን ብዙም ውጤታማ  አይሆንም፤ አንቺም በተስፋ መታገል አለብሽ፡፡ ከዚህ ውጥረት በአፋጣኝ እራስሽን ማላቀቅ አለብሽ ምን መሰለሽ ውጥረት ከቁጥጥራችን ውጭ ከወጣ ወደ ስራ ህይወታችን ይሄድና ስህተት የሆነ ውሳኔ እንድንወስን ያደርገናል፡፡ ከዛም አልፎ የቤተሰብ ህይወታችን ላይ ጫና ያሳድራል፡፡ውጥረት ያመጣብንን ችግር በወቅቱና በሰዓቱ ካልተቆጣጠርነው እዕምሯችንና አካላችንን ይቆጣጠርና የጤና ችግር ከማስከተሉም በላይ አካላዊ በሽታና አእምሮአዊ በሽታ ያስከትልብናል..በሂደትም ለባህሪ ለውጥ ይዳርገናል፡፡ የባህሪ ለውጥ ማለት ደግሞ የምናስብበት መንገድ ነገሮችን የምናይበትና የምንመዝንበት ሚዛን እየተቀየረና እየተዛባ ይሄዳል ማለት ነው፡፡ ያ ደግሞ በውሳኔያችን ላይ ለውጥ ያመጣል፡፡ በስተመጨረሻም የሕይወታችንን መስመር ሙሉ ለሙሉ የመቀየር አቅም ይኖረዋል፡፡ስለዚህ በአእምሮችን ላይ የሚከሰት ማንኛውንም ውጥረት በጊዜና በሰአቱ ማከም ይጠበቅብናል፡፡ ለዛ ነው የምጨቀጭቅሽ››

‹‹እሺ ዶ/ር እሞክራለሁ..ማለቴ ለጤናዬ እፋለማለሁ››

አዎ እንደዛ ማድረግ አለብሽ…አየሽ ራሳችን ከውስጣችን ጋር ስናጣምር ህይወት ምን ያህል ንፁህ በደስታ የተሞላችና ህመም አልባ እንደሆነች  እንረዳለን፡፡ለአዕምሯችን ማንኛውንም አይነት ጥያቄ ብናቀርብለት ያለማቅማማት መልስ ይሰጠናል፡፡ ጥያቄው ብዛትም ሆነ ክብደት ችግር የለውም ብቻ ሁሌ መልስ አያጣም፡፡ ችግሩ መልሱ ትክክል ሊሆንም ላይሆንም ይችላል..ስለዚህ እኛም ራሳችንን የምንጠይቅበት ሆነ ሌሎች የሚጠይቁንን ጥያቄዎች  መጠንቀቅ አለብን፡፡ ምክንያቱም አዕምሯችን የሚሰጠን መልስ በምናቀርብለት የጥያቄ ይዘት ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ ለምሳሌ ይህች ሀገር ወዴት እየሄደች ነው? የሚል ጥያቄ ለአዕምሯችን ቢቀርብለት ቀድሞ የሚመጣለት መልስ ስለጦርነት፤ስለኑሮ ውድነትና፤መሰል ነገሮች ነው...መልሱም በዛ ዙሪያ የሚሽከረከር ነው የሚሆነው፡፡ በተለየ መንገድ ደግሞ ኢትዬጵያ ላንቺ ምንሽ ነች? ቢሆን ጥያቄው...ስለውበቷ፤ ስለ
👍567😁2
ወንዝና ሸንተረሯ..ስለወግና ባህሏ ነው ቀድሞ የሚታሰበው፣..እና አዕምሮሽን ስለምትቀልቢው ሀሳብ ጥንቃቄ አድርጊ …ይሄም የህክምናው አንዱ ዘዴ ነው፡፡ይሄንና መስል ብዙ ብዙ ነገር ለሁለት ሰዓት አወሩና በሌላ ቀጠሮ ተለያዩ ..

ቀጥታ ከሆስፒታል ወጥታ ደራሲ ጳውሎስን  ለማግኘት  ነው  የሄደችው፡፡ ብዙም ሰው የማያዘወትርበት ቦታ ተገናኙና የጨረሰውን መፅሀፍ ከነ  ላፕቶፑ አስረካባት…ሌላ 50 ሺ ብር ሰጠችውና እንዴት እንዳስተካከለው አንብባው የተሰማትን በስልክ እንደምትነግረውና  ቀጣይ  ሂደቶችንም  በዛው  አውርተው እቅድ እንደሚያወጡ ተነጋገሩና ተለያዩ፡፡ ከዛ ወደቤት ነበር የሄደችው፡፡ ቀናው ከፈተላት ..መኪናዋን ቦታዋ አቆመችና ወደመኝታ ቤቷ  ተንደረደረች..ልብሷን ቀያይራ ፒጃማ ለብሳ አልጋዋ ላይ ወጣች…ትራሷን አስተካክላ ላፕቶፑን አበራችና…የመፅሀፉን ረቂቅ ከፈተች..ማንበብ ቀጠለች ስትጀምር ከቀኑ 7 ሰዓት ነበር….ከምሽቱ ሶስት ሰዓት አገባደደች…ወዲያው ስልኳን አነሳችና ደወለች
‹‹ሄሎ በጣም ድንቅ አድርገህ ነው ያስተካከልከው››
‹‹አነብበሽ ጨረስሺው?››
‹‹አዎ አሁን እንደጨረስኩ ነው የደወልኩልህ አድናቆቴን በትኩሱ ልንገርህ ብዬ ነው፡፡ በል ደህና እደር ሰሞኑን እደውልልሀለው፡፡›› አለችውና ወደመታጠቢያ ክፍል ገባች እጇን በመታጠብ ቅድም ሰራተኛዋ አለም ጠረጴዛ ላይ አስቀምጣለት የሄደችውን እራት ክዳኑን ከፍታ መብላት ጀመረች… ለደሰታዋም የወይን ጠርሙሷን ከፍታ ወደ ብርጭቆ አንደቀደቀችና ጠቀም አድርጋ ላፈችለት…ራቱን በልታ እንደጨረሰች የወይኑን ብርጭቆ በአንድ እጇ  ጠርሙሱን በሌላው ይዛ እዛው ፎቅ ላይ ወደአለው በረንዳ ሄደችና ቁጭ ብላ ከኪሷ ስልኳን በማውጣት ሌላ ሰው ጋር ደወለች፡፡
‹‹ሄሎ…በማታ ስለደወልኩ ይቅርታ››
ችግር የለውም..በማንኛውም ሰዓት ብትደውይ በደስታ አነሳዋለሁ››
አመሰግናለሁ...እንግዲህ.ባለፈው እንደነገርኩህ ትልቅ.ውለታ ነው የምጠይቅህ.
‹‹ምነው መፀሀፉ አለቀ እንዴ?››
‹‹አዎ ጥንቅቅ ብሎ አልቋል፡፡
‹‹እሺ..እና ምን አሰብሽ?››

‹‹ነገ ጥዋት ረቂቁንም ቀብዱንም አስረክብሀለሁ…ደራሲውም በፈለከው ሰዓት መጥቶ ውሉን ይፈርምልሀል..ከዛ በጣም በፍጥነት በተመሳሳይ ደግሞ ፍፁም ምስጢራዊ በሆነ መንገድ እንዲታተምልኝ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹ቸግር.የለውም…ምስጢራዊነቱን ለራሴ ደህንነት ስል ነው የምጠብቀው፡፡ ለፍጥነቱ ሁለት ሳምንት ብቻ ነው የማስጠብቅሽ››

‹‹ይሁን …..ቻው በል ጠዋት እንገናኛለን.እደውልልሀለሁ››

‹‹ቻው ደህና እደሪ››ስልኩ ተዘጋ፡፡የወይን ብርጭቆዋን አነሳችና ገርገጭ አድርጋ ጠጣች…በእርካታ.ግንባሯን ወደ ላይ  እንጋጣ አይኖቿን  ሰማዩ  ላይ ሰካች ጨረቃ  ግማሽ    ነች….ኮከቦቹ    በዙሪያዋ  ተበትነዋል…እነሱን.በአድናቆት እየተመለከተች ድንገት  ሳታስበው ወደ ትናንቷ ተመለሰች…ወደአለፈ ትዝታዋ

💫ይቀጥላል💫

ቤተሰቦች እባካችሁ #Subscribe እያደረጋቹ።
#Share #like and #subscribe my #YouTube 

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍585