#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሰሎሞን ድቅቅ ካደረገው እንቅልፍ ቢነቃም
ዓይኖቹ አልገለጥ ስላሉት አሻሽቶ ሊያነቃቸው
ፈልጐ ቀኝ እጁን ለማንቀሳቀስ ሲሞክር
አልተቻለውም፤የሆነ እጁ ላይ የተጫነ ነገር አለ፤የሆነ ሰው አቅፎል..‹‹ወይ እዳዬ !!ማታ ተሳሳትኩ መሰለኝ... ሴት ይዤ ገብቼያለሁ ማለት ነው፡፡›› ሲል አሰበ፤ እሱን ተወውና
ግራውን ሞከረ ተመሳሳይ ነው፡፡በዚህን ጊዜ ደነገጠ ..እንዴት ሁለት ሴት ልገዛ እችላለው?›› ድንጋጤው አይኖቹ ተበርግደው እንዲከፈቱ አገዘው ፡፡ወደ ቀኙ ዞረና አየ…..ልጁ ዕፀ-ህይወት ናት ዝርግትግት ብላ ክንዱን
ተንተርሳ በነጻነት ተኝታለች...ወደ ግራው
ዞረ..ሌለኛዋ ልጁ ዕፀ‐ፍቅር በተመሳሳይ ሁኔታ ግራ ክንዱ ላይ ተመቻችታ ተኝታለች፡፡ከእሷ ቀጥሎ ቢጃማ ለባሽ የሆነች ገዘፍ ያለች ሴት ከአንሶላው ሳትወጣ ቁጭ ብላ መፅሀፍ
እያነበበች ነው፡፡
‹‹የፈጣሪ ያለህ!!››አለ የልጆቹ ሲገርመው ከአመታት በፊት የፈታት ሚስቱን ከጎኑ ሲመለከት፡፡ ‹‹ምን ልትሰራ እሱ ቤርጓ ተገኘች?..የቤቱን ዙሪያ ገባ በግርምት ቃኘ... ቤርጎው አይደለም ያለው ፤ የድሮ ቤቱ... የበፊት መኝታው ክፍሉ ውስጥ..የበፊት አልጋው ላይ ከበፊት ሚስቱ ጋር…የሚገርም ጉዳይ ነው፡፡
‹‹እየቃዠው መሆን አለበት?››ድምፅ አውጥቶ ተናገረ፡፡
የውብዳር የተናገረውን በትክክል አጥርታ ባትሰማም የሆነ ነገር እንዳለ ድምፁ ጆሮዋ ጋር ስለደረሰ የምታነበውን መጽሀፍ ቅዱስ በመክደን ያቀረቀረ ግንባሯን ወደ ላይ ቀና አደረገችና << ነቃህ እንዴ….?እንዴት ነው ሰላም አደርክ?››አለችው በፍጹም ትህትና ፡፡
ለእሷ ጥያቄ መልስ ከመስጠት ይልቅ የራሱን ጥያቄ አስቀደመ ‹‹የት ነው ያለሁት?››ጠየቃት፡፡
‹‹ቤትህ ነዋ፡፡››
እንደመበርገግ አለና ልጆቹን ከክንዶቹ ላይ አንሻራቶ እራሱን ነጻ በማድረግ ከእሷ ጋር በተመሳሳይ ሁኔታ ተቀመጠ፡፡
‹‹ቀስ... ቀስ.. ልጆቸህን ትቀሰቅሳቸዋለህ››አለችው በለሆሳሳ፡፡
‹‹ቆይ ማታ ሰክሬ ነው አይደል የመጣሁት .. ? በጣም እረበሽኳችሁ እንዴ....? ስትረብሽ ልጆችህም አይተውህ ነበር እንዳትይኝ ብቻ… አዝናለሁ፡፡ እንዲህ ለማድረግ ፈልጌ አልነበረም፡፡ ትንሽ ተበሳጭቼ ስለነበር በዛ ላይ መጠጥ አብዝቼ ስወስድበት እራሴን አስቶኝ ነበር ማለት ነው..አንቺም እኮ ትክክል አይደለሽም፤ስመጣ ዝም ብለሽ ታስገቢኛለሽ እንዴ…? ገና ከውጭ በራፍን አልፌ ሳልገባ ዘበኛው እንዲመልሰኝ አታደርጊም ነበር?››
ዝም ብላ በፍዘት ስታዳምጠው ከቆየች በኃላ << ማታ ስለሆነው ሁሉ ምንም ነገር አታስታውስም ማለት ነው?›.አለችው፤ የሆነ ሀይለኛ የሚቀስፍ ስጋት እና የሚቀዘቅዝ ፍርሀት በሰውነቷ እየተሰራጨባት፡፡
‹‹ቆይ ቆይ..ማታ እኔ ቤርጎ አንቺ…››የሆነ እንደህልም አይነት ትዝታ በአዕምሮዎ ብልጭ ድርግም አለበት፡፡
‹‹አዎ መጥቼ ነበር፡፡››
‹‹አዎ እንደ እሱ በይኝ.. እንጂማ ያን ያህል ላብድ አልችልም፡፡ >>
‹‹የምን እብደት አመጣህብኝ?››
‹‹...ቀጥታ ዝም ብዬ እዚህ በመምጣት ካላደርኩ አልልማ ... አንቺን እዛ ሳይ ተከትዬሽ መጥቼ እንጂ..፡››
‹‹እንደዛም አይደለም፡፡››
‹‹ታዲያ እንዴት ነው?››
‹‹እኔ ነኝ ለምኜህ ማለት ይቅርታ ጠይቄህ ይዤህ የመጣሁት...››
‹‹እየቀለድሽ አይደለም አይደል?››
‹‹እውነቴን ነው ሶል... ተነጋግረን ተስማምተን ነበር የመጣሀው፡፡ጥፋት ያጠፋህ መስሎ ከተሰማህ እንኳን ጥፋቱ የእኔ ነው እንጂ ያአንተ አይደለም፡፡ አንተ ምንም አላደረግክም …እኔም ግን ወድጄ አይደለም ፤ እስቲ ልጆቻችንን እያቸው፤ዛሬ ከጎናቸው ብትሆን እንዴት የሰላም እንቅልፍ እንደተኙ.. አቤት ማታ ቀስቅሰህ መጥቼያለሁ ስትላቸው የተደሰቱት መደሰት ልነግርህ አልችልም..ታዲያ ለእነሱ ስትል ይቅር ብትለኝ ምን አለበት..?በቃ ምንም ልበድልህ ... ምንም ላጥፋ ለእነሱ ስትል ልትረሳልኝ አትችልም?››
‹‹ኧረ ቆይ.. አንቺ ባጠፋሽው መጠን እኮ እኔም አጥፍቼያለሁ›..
‹‹ታዲያ በቃ ይቅር እንባባላ..በቃ በስካር
መንፈስም ቢሆን ወደ ቤትህ አንዴ ገብተሀል
..በፈጠረህ በዚህ በምታምንበት መጽሀፍ
ቅዱስ ልለምንህ ፤ ተመልሰህ ከቤትህ
አትውጣ... ከልጆችህ ጋር ኑር...አንተ
ከምትወጣ እኔ ብወጣ ይሻለኛል...ሴት ልጆች
አባታቸውን አብልጠው ይወዳሉ ሲባል አባባል
ብቻ ይመስለኝ ነበር..በራሴ ልጆች ነው እውነት
መሆኑን ያረጋገጥኩት... አንተን አጥተው መኖር
በጣም ነው የሚከብዳቸው... ስለዚህ
ባክህ..ባክህ››በማለት በቃላትም ...በአይኖቿ
እርግብግብታም ተለማመጠችው፡፡እጁን ላካና አቅፎ ወደ ራሱ በመጎተት ደረቱ ላይ ለጥፎት በጆሮዋ ‹‹እኔም የትም አልሄድ ..አንቺ
እንዳልሽው በቃ ያለፈውን እንርሳው... የውሾን
ነገር ያነሳ ውሾ ይሁን››አላት፡፡
‹‹እሺ የእኔ ጌታ አመሰግናለሁ››አለችውና የሚንጠባጠበውን እንባዋን በቀኝ እጇ እያበሰች ከእቅፉ ወጥታ አልጋውን ለቃ ወረደች፡፡በዚህ ጊዜ በመሀከላቸው ያለችው ዕፀ- ህይወት ከእንቅልፏ ባና ዓይኖቿን ከመግለጧ በፊት መጀመሪያ የጠየቀችው ጥያቄ‹‹አባቴስ?›› የሚል ነበር፡፡
‹‹አለሁልሽ የእኔ ቆንጆ >> ብሎ ወደ ራሱ አስጠግቶ አቀፋት... ሙሉ በሙሉ ነቃችና እላዩ ላይ ተንጠልጥላ እያገላበጠች ትስመው ጀመር፡፡ በዚህም አረካችም መንታ እህቷንም ቀሰቀሰቻት ..ሰሎሞን ተይ ትተኛ ቢላትም ልታዳምጠው አልፈለገችም፡፡ ሁለቱም ልጆቹ ለመጀመሪያ ቀን ያዩት ይመስል ትንፋሽ እስኪያጥረው እና ድክም እሲኪለው ተላፉት ፣ሳሙት፣እላዩ ላይ ጨፈሩ፡፡ በመጨረሻ የውብዳር ነበረች በግድ አላቃ ለቁርስ መኝታ ቤቱን ለቀው ወደ ምግብ መመገቢያ ቤት እንዲሄዱ ያስገደቻቸው፡፡
በፊት አብሯቸው ይኖር በነበረበት በመጀመሪያዎቹ የፍቅር ዓመታት በእጇ ትሰራለት የነበረውን እና እሱም በጣም እየወደደውና እሷንም እያመሰገነው ይበላው የነበረውን ምግብ ነበር ሰርታ ለቁርስ ያቀረበችው ፡፡በሳቅ እና በጨወታ ታጅበው
ቁርሳቸውን እየበሉ ግማሽ እንደደረሱ የሳሎኑ በራፍ ተንኳኳ፡፡
‹‹ይግቡ ..ክፍት ነው›› አለች የውብዳር ከመቀመጫዋ ሳትነሳ.፡
በራፉ ተከፈተ..ሁሴን ነበረ የመጣው ፡፡
‹‹እየተጣራጠርኩ ነው የመጣሁት ስልክሽ አይሰ......››ንግግሩን አቋረጠ፡፡እርምጃውንም መሀል ሳሎን ላይ ገታው፡፡የሰሎሞን እዛ ቤት ውስጥ መገኘት ፍጽም ከግምቱ ውጭ የሆነ ክስተት ነበር... የሆነ ውሽማው ቤት ሊሰርቅ የሄደ ሰው ከባልዬው ጋር የመፋጠጥ አጋጣሚ እንዳጋጠመው ሰው ነው አደነጋገጡ፡፡
<< ና እንጂ ....አንተ እንወድሀለን ማለት ነው .. ቁርስ ላይ ደረስክ.…‹ሲበሉ አድርሰኝ ሲጣሉ መልሰኝ› የሚባለው እንደዚህ ነው››አለችው የውብዳር፡፡
ሁሴን ግን የእሷን ወሬ አልሰማም‹‹ይሄ ሰውዬ
እዚህ ምን ይሰራል? ››አላት እንደምንም እግሮቹን አነቃንቆ ወደ እነሱ እየተጠጋ።
‹‹እቤቱ ከልጆቹ እና ከሚስቱ ጋር ቁጭ ብሎ ቁርስ እየበላ ነዋ››
‹‹..ከልጆቹ እና ከሚስቱ ጋር >> ልትል አስባ ነበር ያልተረጋገጠውን የሚስትነት ማዕረጓን መልሳ የዋጠችው›› የምታድርበት ሆቴል እኮ ሁለቴ ነዋ የመጣሁት ስልክህም ዝግ ነው ..ግራ ሲገባኝ ጊዜዬን ከማባክን እነዚህ ልጆች ልይ ብዬ ወደ እዚህ ጎራ ማለቴ እኮ ነበር..እንጂማ.. ››በማለት ለልጆች ይዞላቸው የመጣውን ቸኮሌት አከፋፈሏቸው ወንበር ስቦ ተቀመጠ ፤አመስግነው ተቀበሉት፡፡
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሰሎሞን ድቅቅ ካደረገው እንቅልፍ ቢነቃም
ዓይኖቹ አልገለጥ ስላሉት አሻሽቶ ሊያነቃቸው
ፈልጐ ቀኝ እጁን ለማንቀሳቀስ ሲሞክር
አልተቻለውም፤የሆነ እጁ ላይ የተጫነ ነገር አለ፤የሆነ ሰው አቅፎል..‹‹ወይ እዳዬ !!ማታ ተሳሳትኩ መሰለኝ... ሴት ይዤ ገብቼያለሁ ማለት ነው፡፡›› ሲል አሰበ፤ እሱን ተወውና
ግራውን ሞከረ ተመሳሳይ ነው፡፡በዚህን ጊዜ ደነገጠ ..እንዴት ሁለት ሴት ልገዛ እችላለው?›› ድንጋጤው አይኖቹ ተበርግደው እንዲከፈቱ አገዘው ፡፡ወደ ቀኙ ዞረና አየ…..ልጁ ዕፀ-ህይወት ናት ዝርግትግት ብላ ክንዱን
ተንተርሳ በነጻነት ተኝታለች...ወደ ግራው
ዞረ..ሌለኛዋ ልጁ ዕፀ‐ፍቅር በተመሳሳይ ሁኔታ ግራ ክንዱ ላይ ተመቻችታ ተኝታለች፡፡ከእሷ ቀጥሎ ቢጃማ ለባሽ የሆነች ገዘፍ ያለች ሴት ከአንሶላው ሳትወጣ ቁጭ ብላ መፅሀፍ
እያነበበች ነው፡፡
‹‹የፈጣሪ ያለህ!!››አለ የልጆቹ ሲገርመው ከአመታት በፊት የፈታት ሚስቱን ከጎኑ ሲመለከት፡፡ ‹‹ምን ልትሰራ እሱ ቤርጓ ተገኘች?..የቤቱን ዙሪያ ገባ በግርምት ቃኘ... ቤርጎው አይደለም ያለው ፤ የድሮ ቤቱ... የበፊት መኝታው ክፍሉ ውስጥ..የበፊት አልጋው ላይ ከበፊት ሚስቱ ጋር…የሚገርም ጉዳይ ነው፡፡
‹‹እየቃዠው መሆን አለበት?››ድምፅ አውጥቶ ተናገረ፡፡
የውብዳር የተናገረውን በትክክል አጥርታ ባትሰማም የሆነ ነገር እንዳለ ድምፁ ጆሮዋ ጋር ስለደረሰ የምታነበውን መጽሀፍ ቅዱስ በመክደን ያቀረቀረ ግንባሯን ወደ ላይ ቀና አደረገችና << ነቃህ እንዴ….?እንዴት ነው ሰላም አደርክ?››አለችው በፍጹም ትህትና ፡፡
ለእሷ ጥያቄ መልስ ከመስጠት ይልቅ የራሱን ጥያቄ አስቀደመ ‹‹የት ነው ያለሁት?››ጠየቃት፡፡
‹‹ቤትህ ነዋ፡፡››
እንደመበርገግ አለና ልጆቹን ከክንዶቹ ላይ አንሻራቶ እራሱን ነጻ በማድረግ ከእሷ ጋር በተመሳሳይ ሁኔታ ተቀመጠ፡፡
‹‹ቀስ... ቀስ.. ልጆቸህን ትቀሰቅሳቸዋለህ››አለችው በለሆሳሳ፡፡
‹‹ቆይ ማታ ሰክሬ ነው አይደል የመጣሁት .. ? በጣም እረበሽኳችሁ እንዴ....? ስትረብሽ ልጆችህም አይተውህ ነበር እንዳትይኝ ብቻ… አዝናለሁ፡፡ እንዲህ ለማድረግ ፈልጌ አልነበረም፡፡ ትንሽ ተበሳጭቼ ስለነበር በዛ ላይ መጠጥ አብዝቼ ስወስድበት እራሴን አስቶኝ ነበር ማለት ነው..አንቺም እኮ ትክክል አይደለሽም፤ስመጣ ዝም ብለሽ ታስገቢኛለሽ እንዴ…? ገና ከውጭ በራፍን አልፌ ሳልገባ ዘበኛው እንዲመልሰኝ አታደርጊም ነበር?››
ዝም ብላ በፍዘት ስታዳምጠው ከቆየች በኃላ << ማታ ስለሆነው ሁሉ ምንም ነገር አታስታውስም ማለት ነው?›.አለችው፤ የሆነ ሀይለኛ የሚቀስፍ ስጋት እና የሚቀዘቅዝ ፍርሀት በሰውነቷ እየተሰራጨባት፡፡
‹‹ቆይ ቆይ..ማታ እኔ ቤርጎ አንቺ…››የሆነ እንደህልም አይነት ትዝታ በአዕምሮዎ ብልጭ ድርግም አለበት፡፡
‹‹አዎ መጥቼ ነበር፡፡››
‹‹አዎ እንደ እሱ በይኝ.. እንጂማ ያን ያህል ላብድ አልችልም፡፡ >>
‹‹የምን እብደት አመጣህብኝ?››
‹‹...ቀጥታ ዝም ብዬ እዚህ በመምጣት ካላደርኩ አልልማ ... አንቺን እዛ ሳይ ተከትዬሽ መጥቼ እንጂ..፡››
‹‹እንደዛም አይደለም፡፡››
‹‹ታዲያ እንዴት ነው?››
‹‹እኔ ነኝ ለምኜህ ማለት ይቅርታ ጠይቄህ ይዤህ የመጣሁት...››
‹‹እየቀለድሽ አይደለም አይደል?››
‹‹እውነቴን ነው ሶል... ተነጋግረን ተስማምተን ነበር የመጣሀው፡፡ጥፋት ያጠፋህ መስሎ ከተሰማህ እንኳን ጥፋቱ የእኔ ነው እንጂ ያአንተ አይደለም፡፡ አንተ ምንም አላደረግክም …እኔም ግን ወድጄ አይደለም ፤ እስቲ ልጆቻችንን እያቸው፤ዛሬ ከጎናቸው ብትሆን እንዴት የሰላም እንቅልፍ እንደተኙ.. አቤት ማታ ቀስቅሰህ መጥቼያለሁ ስትላቸው የተደሰቱት መደሰት ልነግርህ አልችልም..ታዲያ ለእነሱ ስትል ይቅር ብትለኝ ምን አለበት..?በቃ ምንም ልበድልህ ... ምንም ላጥፋ ለእነሱ ስትል ልትረሳልኝ አትችልም?››
‹‹ኧረ ቆይ.. አንቺ ባጠፋሽው መጠን እኮ እኔም አጥፍቼያለሁ›..
‹‹ታዲያ በቃ ይቅር እንባባላ..በቃ በስካር
መንፈስም ቢሆን ወደ ቤትህ አንዴ ገብተሀል
..በፈጠረህ በዚህ በምታምንበት መጽሀፍ
ቅዱስ ልለምንህ ፤ ተመልሰህ ከቤትህ
አትውጣ... ከልጆችህ ጋር ኑር...አንተ
ከምትወጣ እኔ ብወጣ ይሻለኛል...ሴት ልጆች
አባታቸውን አብልጠው ይወዳሉ ሲባል አባባል
ብቻ ይመስለኝ ነበር..በራሴ ልጆች ነው እውነት
መሆኑን ያረጋገጥኩት... አንተን አጥተው መኖር
በጣም ነው የሚከብዳቸው... ስለዚህ
ባክህ..ባክህ››በማለት በቃላትም ...በአይኖቿ
እርግብግብታም ተለማመጠችው፡፡እጁን ላካና አቅፎ ወደ ራሱ በመጎተት ደረቱ ላይ ለጥፎት በጆሮዋ ‹‹እኔም የትም አልሄድ ..አንቺ
እንዳልሽው በቃ ያለፈውን እንርሳው... የውሾን
ነገር ያነሳ ውሾ ይሁን››አላት፡፡
‹‹እሺ የእኔ ጌታ አመሰግናለሁ››አለችውና የሚንጠባጠበውን እንባዋን በቀኝ እጇ እያበሰች ከእቅፉ ወጥታ አልጋውን ለቃ ወረደች፡፡በዚህ ጊዜ በመሀከላቸው ያለችው ዕፀ- ህይወት ከእንቅልፏ ባና ዓይኖቿን ከመግለጧ በፊት መጀመሪያ የጠየቀችው ጥያቄ‹‹አባቴስ?›› የሚል ነበር፡፡
‹‹አለሁልሽ የእኔ ቆንጆ >> ብሎ ወደ ራሱ አስጠግቶ አቀፋት... ሙሉ በሙሉ ነቃችና እላዩ ላይ ተንጠልጥላ እያገላበጠች ትስመው ጀመር፡፡ በዚህም አረካችም መንታ እህቷንም ቀሰቀሰቻት ..ሰሎሞን ተይ ትተኛ ቢላትም ልታዳምጠው አልፈለገችም፡፡ ሁለቱም ልጆቹ ለመጀመሪያ ቀን ያዩት ይመስል ትንፋሽ እስኪያጥረው እና ድክም እሲኪለው ተላፉት ፣ሳሙት፣እላዩ ላይ ጨፈሩ፡፡ በመጨረሻ የውብዳር ነበረች በግድ አላቃ ለቁርስ መኝታ ቤቱን ለቀው ወደ ምግብ መመገቢያ ቤት እንዲሄዱ ያስገደቻቸው፡፡
በፊት አብሯቸው ይኖር በነበረበት በመጀመሪያዎቹ የፍቅር ዓመታት በእጇ ትሰራለት የነበረውን እና እሱም በጣም እየወደደውና እሷንም እያመሰገነው ይበላው የነበረውን ምግብ ነበር ሰርታ ለቁርስ ያቀረበችው ፡፡በሳቅ እና በጨወታ ታጅበው
ቁርሳቸውን እየበሉ ግማሽ እንደደረሱ የሳሎኑ በራፍ ተንኳኳ፡፡
‹‹ይግቡ ..ክፍት ነው›› አለች የውብዳር ከመቀመጫዋ ሳትነሳ.፡
በራፉ ተከፈተ..ሁሴን ነበረ የመጣው ፡፡
‹‹እየተጣራጠርኩ ነው የመጣሁት ስልክሽ አይሰ......››ንግግሩን አቋረጠ፡፡እርምጃውንም መሀል ሳሎን ላይ ገታው፡፡የሰሎሞን እዛ ቤት ውስጥ መገኘት ፍጽም ከግምቱ ውጭ የሆነ ክስተት ነበር... የሆነ ውሽማው ቤት ሊሰርቅ የሄደ ሰው ከባልዬው ጋር የመፋጠጥ አጋጣሚ እንዳጋጠመው ሰው ነው አደነጋገጡ፡፡
<< ና እንጂ ....አንተ እንወድሀለን ማለት ነው .. ቁርስ ላይ ደረስክ.…‹ሲበሉ አድርሰኝ ሲጣሉ መልሰኝ› የሚባለው እንደዚህ ነው››አለችው የውብዳር፡፡
ሁሴን ግን የእሷን ወሬ አልሰማም‹‹ይሄ ሰውዬ
እዚህ ምን ይሰራል? ››አላት እንደምንም እግሮቹን አነቃንቆ ወደ እነሱ እየተጠጋ።
‹‹እቤቱ ከልጆቹ እና ከሚስቱ ጋር ቁጭ ብሎ ቁርስ እየበላ ነዋ››
‹‹..ከልጆቹ እና ከሚስቱ ጋር >> ልትል አስባ ነበር ያልተረጋገጠውን የሚስትነት ማዕረጓን መልሳ የዋጠችው›› የምታድርበት ሆቴል እኮ ሁለቴ ነዋ የመጣሁት ስልክህም ዝግ ነው ..ግራ ሲገባኝ ጊዜዬን ከማባክን እነዚህ ልጆች ልይ ብዬ ወደ እዚህ ጎራ ማለቴ እኮ ነበር..እንጂማ.. ››በማለት ለልጆች ይዞላቸው የመጣውን ቸኮሌት አከፋፈሏቸው ወንበር ስቦ ተቀመጠ ፤አመስግነው ተቀበሉት፡፡
👍68❤8
እጁን ታጠበና ማዕዱን አብሯቸው መቋደሰ ጀመረ... የውብዳር ልታጎርሰው ስትል ‹‹ኧረ እዛው የጀመርሽውን አጉርሺ..››አላት፡፡
‹‹ወደ ቤቴ በመመለሴ ተበሳጨህ እንዴ ?››አለው ሰሎሞን እየሳቀ፡፡
‹‹መበሳጨት አይደለም ....ግን ስርዓትና ደንብ ጣሳችሁ ማለቴ ነው ፡፡እንዲሁ ለሞራላችን
እንኳን የውሸት ሽማግሌ አድርጋችሁን <እኛ ነን
እኮ ያስታረቅናቸው> ብለን ትንሽ ብንጎርር ምን
አለበት…?ደግሞ እኮ ቀጠሮ ስላለን ሁለት ሰዓት ነበር ሆቴልህ የደረስኩት በህልም
አይተሀቸው ነጋ አልነጋ ብለህ ነው እንዴ ዶሮ
ሳይጮኽ የመጣኸው?››
‹‹ኧረ ምን ደሮ ሳይጮኸ ..ወገግ ብሎ ሲነጋ አይኖቼን ስገልጥ እዚሁ ቤት የገዛ መኝታ ቤት ከሙሉ ቤተሰቤ ጋር በአንድ አልጋ ላይ ተኝቼ እራሴን አገኘሁት፡፡››
‹‹ኧረ ባክህ በቃ!!! ለሊት ከተኛህበት አፍነው አምጥተውህ ነዋ፡፡››
‹‹መሰለኝ... እስቲ እሷን ጠይቃት፡፡ >>
‹‹ይሄንን ሁለታችሁንም በተናጥል ለየብቻ ነው የምጠይቃችሁ...አሁን ወደ ውጭ ትወጣለህ ወይስ እዚሁ ነው የምትወለው?››
‹‹ኧረ እወጣለሁ... 5 ሰዓት አንድ የምደርስባት ቦታ አለቺኝ›.እጃቸውን ተጣጥበው ተነሱ፡፡
‹‹እንዴ አባ ለምን ትሄዳለህ? አትሂድ፡፡››
‹‹አልሄድም ... ስራ ደርሼ ልመጣ ነው፡፡››
‹‹ዛሬም እኛ ጋር አዚህ ነው የምታድረው ?>>
‹‹አዎ.. ከአሁን ወዲህ ሁል ግዜ እናንተ ጋር ነው የማድረው ..እዚሁ ነው የምኖረው››አረጋገጠላቸው፡
‹‹እንወድሀለን አባ፡፡›› ሁለቱም በአንድ ላይ ወደ ታች አስጎንብሰውት ግራና ቀኝ ጉንጩን ተከፋፍለው ሳሙትና ሸኙት፡፡
የውብዳር ፈራ ተባ እያለች‹‹ለምሳ ብቅ ትላላችሁ እንዴ?›› ስትል ጠየቀች ፡፡
‹‹አዎ የእሱን አላውቅም እኔ ግን እመጣለሁ..ልክ ስድስት ሰዓት ተኩል ላይ ከች እላለሁ..ያቺ ቡናሽን አፍልተሸ የምትጠብቂኝ ከሆነ?
‹‹ግድ የለህም አንተ ብቻ ና..ሁስ አንተስ..?››አለችው ፈዞ ሁኔታቸውን በትኩረት ሲመለከታቸው የነበረውን ጓደኛቸውን፡፡
‹‹ኧረ እኔ ዛሬ ይዝለለኝ፤ይስፋችሁ >>ብሎ ተሰናበታትና ቀድሞት ወደ መኪናው አመራ.. ሰሎሞንም ተከትሎት የገቢናውን በር ከፍቶ ወደ ውስጥ ሊገባ ሲል የውብ ዳር‹‹ ሶል ››ብላ ተጣራች ፡፡
‹‹ሆቴል ብሄድ እቃዎችህን ይሰጡኛል እንዴ?››
‹‹ግድ የለም እኔ ለምሳ ስመጣ ይዤው እመጣለሁ…ደና ዋይልኝ፡፡››
‹‹እሺ ደህና ዋል››አለችው፡፡
ግቢውን ለቀው እንደወጡ‹‹አንተ ጉደኛ ማታ እርም የሴት ቀሚስ ብገልብ እያልክ ስትምል ስትገዘት አልነበረም እንዴ?››
‹‹ታዲያ መች ገለብኩ?››
<<ማለት?>>
‹‹ማለትማ አዲስ ቀሚስ አልገልብም አልኩህ እንጂ ድሮም የእኔ የነበረውን ቀሚስ አልነካም ብዬ አልማልኩም፡፡››
‹‹አይ አንተ መቼስ ማምለጫ አታጣ....ያም ሆነ ይህ ግን በሆነው ነገር በጣም ደስ ብሎኛል፡፡በተለይ ከልጆችህ አንፃር በዚህ ውሳኔህ ብትፀና እኔ ደስተኛ ነኝ..፡፡››
‹‹በቃ አየውት እኮ .. ሁሉንም ፍላጐቶችህን የምታሟላልህ እንከን አልባ ሴት የትም አታገኝም.. እዚህም ቤት ያለው እሳት መልኩን ቀይሮ እዛም ቤት አለ ፡፡ዋናው ተቻችሎ የአንዱን ጉድለት አንዱ ሞልቶ.. አንዱ ሲያጠፋ
አንዱ ይቅር ብሎ. ህይወትን እየተጋገዙ መኖር ነው..፡፡››
‹‹አሪፍ ነው..ይህቺ እንግዲህ ስሜት ያልነካካት ከህይወት ልምድ የተገኘች ጠቃሚ እውቀት ነች››አለና ለሰሎሞን ንግግር ድጋፍ ሰጠው ፡፡በመጀመሪያ የተጓዙት ሰሎሞን አርፎበት ወደነበረው ሆቴል ነው፤ ዕቃውንም እዛ የቆመችውንም መኪናውን ለመውሰድ፡፡ ደርሰው እንደቆሙ ሁሴን ሞባይሉን አነሳና ደወለ..::
‹‹ሄሎ ፍቅር..አንድ አስደማሚ ወሬ ልነግርሽ ነው››ሰሎሞን አንጓጠጠው፡፡
‹‹ጋዜጠኞች ስትባሉ ወሬ ተቀብሎ በአየር ለመበተን ሚቀድማችሁ የለም..ለምን
አንደኛህን በጋዜጣህ አታሳትመውም፡፡››ብሎት ጥሎት የፎቁን ደረጃ መውጣት ጀመረ፤ሁሴንም ችላ ብሎት ከትንግርት ጋር ማውራቱን ቀጠለ፡፡
‹‹ምንድነው.. ?ምን ሰማህ?››
‹‹ሰሎሞን ነዋ፡፡››
‹‹ሰሎሞን ምን ሆነ?
‹‹ታረቀ እኮ፡››
‹‹አንተ እውነትም ደስ የሚል ቦንብ ወሬ ነው የነገርከኝ... ግን እንደዛ ክርር አድርጋው አልነበር እንዴ እንዴት ሀሳቧን ቀየረች..? ይገርምሀል እኔ እራሴ ከሶስት ቀን በፊት እቤቷ ድረስ ሄጄ ለምኛት ነበር....እንዴት መሰለህ ሲያንዘረዝራት የነበረው...ለማንኛውም እንኳን ታረቁ::>>
‹‹ስለማን ነው የምታወሪው…..?ከየውብዳር ጋር እኮ ነው የታረቁት፡፡››
‹‹የውብ ዳር? >>
‹‹አዎ ከውብዳር ጋር፡፡››
‹‹እንዴት ሆኖ?››
‹‹ዝርዝር መረጃው ገና አልደረሰኝም ግን ያው አደገኛ የፍቅር ግርሻ እንደመጋኛ ሁለቱንም አጠናግሯቸዋል፡፡ >>
‹‹በጣም ደስ ይላል ...በቃ በእናትህ ለምን እራት አንጋብዛቸውም፡፡››
‹‹የት.. ?ቤት ?››
‹‹ቤት እማ ትንሽ ይከብዳል ሆቴል››
‹‹አሪፍ ሀሳብ ነው ... ሰባት ሰዓት አካባቢ ተገናኝተን ስለወጪ መጋራቱ እናውራበታለን፡፡››
‹‹ችግር የለውም ይመቸኛል.. ስትፈልገኝ ቢሮ ና ::>>
‹‹እሺ ቻው ፍቅር፡፡››
‹‹ቻው..አፈቅርሀለሁ፡፡››
‹‹እኔም፡፡››
ስልኩን ዘግቶ ሰሎሞን የሚታገዝ ዕቃ ካለው ሊያግዘው ፎቅ ወደ ሚገኘው መኝታ ክፍሉ የሚወስደውን ደረጃ መውጣት እንደጀመረ ሞባይሉ ጮኸ..መጓዙን ሳያቆም አነሳው‹‹ሄሎ ዶክተር፡፡››
‹‹ሁሴን ሰላም ነህ?››
‹‹ሰላም ነኝ አንቺስ እንዴት ነሽ?››
‹‹ይመስገነው ሰሞኑን ትንሽ የስራ ውጥረት ስለነበረ ነው ላገኝህ ያልቻልኩት.. ዛሬ ከአስራአንድ ሰዓት በኃላ ነፃ ነኝ አንተን የሚመችህ ከሆነ…፡፡››
<<ችግር የለም ይመቸኛል..የት እንገናኝ፡፡››
‹‹ግዮን ቢሆን ይመቸኛል፡፡››
‹‹በቃ እዛው በሰዓቱ እደርሳለሁ፡፡››
‹‹እሺ አመሰግናለሁ ሁሴን፡፡››
‹‹እሺ ቻው ዶ/ር ሶፊያ››
ቤተሰቦች በቅናነት #YouTube #subscribe እያደረጋቹ በጣም ቀንሳችኋል 1ደቂቃ አይፈጅም ገብታችሁ #Subscribe አድርጉ አመሰግናለሁ።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹ወደ ቤቴ በመመለሴ ተበሳጨህ እንዴ ?››አለው ሰሎሞን እየሳቀ፡፡
‹‹መበሳጨት አይደለም ....ግን ስርዓትና ደንብ ጣሳችሁ ማለቴ ነው ፡፡እንዲሁ ለሞራላችን
እንኳን የውሸት ሽማግሌ አድርጋችሁን <እኛ ነን
እኮ ያስታረቅናቸው> ብለን ትንሽ ብንጎርር ምን
አለበት…?ደግሞ እኮ ቀጠሮ ስላለን ሁለት ሰዓት ነበር ሆቴልህ የደረስኩት በህልም
አይተሀቸው ነጋ አልነጋ ብለህ ነው እንዴ ዶሮ
ሳይጮኽ የመጣኸው?››
‹‹ኧረ ምን ደሮ ሳይጮኸ ..ወገግ ብሎ ሲነጋ አይኖቼን ስገልጥ እዚሁ ቤት የገዛ መኝታ ቤት ከሙሉ ቤተሰቤ ጋር በአንድ አልጋ ላይ ተኝቼ እራሴን አገኘሁት፡፡››
‹‹ኧረ ባክህ በቃ!!! ለሊት ከተኛህበት አፍነው አምጥተውህ ነዋ፡፡››
‹‹መሰለኝ... እስቲ እሷን ጠይቃት፡፡ >>
‹‹ይሄንን ሁለታችሁንም በተናጥል ለየብቻ ነው የምጠይቃችሁ...አሁን ወደ ውጭ ትወጣለህ ወይስ እዚሁ ነው የምትወለው?››
‹‹ኧረ እወጣለሁ... 5 ሰዓት አንድ የምደርስባት ቦታ አለቺኝ›.እጃቸውን ተጣጥበው ተነሱ፡፡
‹‹እንዴ አባ ለምን ትሄዳለህ? አትሂድ፡፡››
‹‹አልሄድም ... ስራ ደርሼ ልመጣ ነው፡፡››
‹‹ዛሬም እኛ ጋር አዚህ ነው የምታድረው ?>>
‹‹አዎ.. ከአሁን ወዲህ ሁል ግዜ እናንተ ጋር ነው የማድረው ..እዚሁ ነው የምኖረው››አረጋገጠላቸው፡
‹‹እንወድሀለን አባ፡፡›› ሁለቱም በአንድ ላይ ወደ ታች አስጎንብሰውት ግራና ቀኝ ጉንጩን ተከፋፍለው ሳሙትና ሸኙት፡፡
የውብዳር ፈራ ተባ እያለች‹‹ለምሳ ብቅ ትላላችሁ እንዴ?›› ስትል ጠየቀች ፡፡
‹‹አዎ የእሱን አላውቅም እኔ ግን እመጣለሁ..ልክ ስድስት ሰዓት ተኩል ላይ ከች እላለሁ..ያቺ ቡናሽን አፍልተሸ የምትጠብቂኝ ከሆነ?
‹‹ግድ የለህም አንተ ብቻ ና..ሁስ አንተስ..?››አለችው ፈዞ ሁኔታቸውን በትኩረት ሲመለከታቸው የነበረውን ጓደኛቸውን፡፡
‹‹ኧረ እኔ ዛሬ ይዝለለኝ፤ይስፋችሁ >>ብሎ ተሰናበታትና ቀድሞት ወደ መኪናው አመራ.. ሰሎሞንም ተከትሎት የገቢናውን በር ከፍቶ ወደ ውስጥ ሊገባ ሲል የውብ ዳር‹‹ ሶል ››ብላ ተጣራች ፡፡
‹‹ሆቴል ብሄድ እቃዎችህን ይሰጡኛል እንዴ?››
‹‹ግድ የለም እኔ ለምሳ ስመጣ ይዤው እመጣለሁ…ደና ዋይልኝ፡፡››
‹‹እሺ ደህና ዋል››አለችው፡፡
ግቢውን ለቀው እንደወጡ‹‹አንተ ጉደኛ ማታ እርም የሴት ቀሚስ ብገልብ እያልክ ስትምል ስትገዘት አልነበረም እንዴ?››
‹‹ታዲያ መች ገለብኩ?››
<<ማለት?>>
‹‹ማለትማ አዲስ ቀሚስ አልገልብም አልኩህ እንጂ ድሮም የእኔ የነበረውን ቀሚስ አልነካም ብዬ አልማልኩም፡፡››
‹‹አይ አንተ መቼስ ማምለጫ አታጣ....ያም ሆነ ይህ ግን በሆነው ነገር በጣም ደስ ብሎኛል፡፡በተለይ ከልጆችህ አንፃር በዚህ ውሳኔህ ብትፀና እኔ ደስተኛ ነኝ..፡፡››
‹‹በቃ አየውት እኮ .. ሁሉንም ፍላጐቶችህን የምታሟላልህ እንከን አልባ ሴት የትም አታገኝም.. እዚህም ቤት ያለው እሳት መልኩን ቀይሮ እዛም ቤት አለ ፡፡ዋናው ተቻችሎ የአንዱን ጉድለት አንዱ ሞልቶ.. አንዱ ሲያጠፋ
አንዱ ይቅር ብሎ. ህይወትን እየተጋገዙ መኖር ነው..፡፡››
‹‹አሪፍ ነው..ይህቺ እንግዲህ ስሜት ያልነካካት ከህይወት ልምድ የተገኘች ጠቃሚ እውቀት ነች››አለና ለሰሎሞን ንግግር ድጋፍ ሰጠው ፡፡በመጀመሪያ የተጓዙት ሰሎሞን አርፎበት ወደነበረው ሆቴል ነው፤ ዕቃውንም እዛ የቆመችውንም መኪናውን ለመውሰድ፡፡ ደርሰው እንደቆሙ ሁሴን ሞባይሉን አነሳና ደወለ..::
‹‹ሄሎ ፍቅር..አንድ አስደማሚ ወሬ ልነግርሽ ነው››ሰሎሞን አንጓጠጠው፡፡
‹‹ጋዜጠኞች ስትባሉ ወሬ ተቀብሎ በአየር ለመበተን ሚቀድማችሁ የለም..ለምን
አንደኛህን በጋዜጣህ አታሳትመውም፡፡››ብሎት ጥሎት የፎቁን ደረጃ መውጣት ጀመረ፤ሁሴንም ችላ ብሎት ከትንግርት ጋር ማውራቱን ቀጠለ፡፡
‹‹ምንድነው.. ?ምን ሰማህ?››
‹‹ሰሎሞን ነዋ፡፡››
‹‹ሰሎሞን ምን ሆነ?
‹‹ታረቀ እኮ፡››
‹‹አንተ እውነትም ደስ የሚል ቦንብ ወሬ ነው የነገርከኝ... ግን እንደዛ ክርር አድርጋው አልነበር እንዴ እንዴት ሀሳቧን ቀየረች..? ይገርምሀል እኔ እራሴ ከሶስት ቀን በፊት እቤቷ ድረስ ሄጄ ለምኛት ነበር....እንዴት መሰለህ ሲያንዘረዝራት የነበረው...ለማንኛውም እንኳን ታረቁ::>>
‹‹ስለማን ነው የምታወሪው…..?ከየውብዳር ጋር እኮ ነው የታረቁት፡፡››
‹‹የውብ ዳር? >>
‹‹አዎ ከውብዳር ጋር፡፡››
‹‹እንዴት ሆኖ?››
‹‹ዝርዝር መረጃው ገና አልደረሰኝም ግን ያው አደገኛ የፍቅር ግርሻ እንደመጋኛ ሁለቱንም አጠናግሯቸዋል፡፡ >>
‹‹በጣም ደስ ይላል ...በቃ በእናትህ ለምን እራት አንጋብዛቸውም፡፡››
‹‹የት.. ?ቤት ?››
‹‹ቤት እማ ትንሽ ይከብዳል ሆቴል››
‹‹አሪፍ ሀሳብ ነው ... ሰባት ሰዓት አካባቢ ተገናኝተን ስለወጪ መጋራቱ እናውራበታለን፡፡››
‹‹ችግር የለውም ይመቸኛል.. ስትፈልገኝ ቢሮ ና ::>>
‹‹እሺ ቻው ፍቅር፡፡››
‹‹ቻው..አፈቅርሀለሁ፡፡››
‹‹እኔም፡፡››
ስልኩን ዘግቶ ሰሎሞን የሚታገዝ ዕቃ ካለው ሊያግዘው ፎቅ ወደ ሚገኘው መኝታ ክፍሉ የሚወስደውን ደረጃ መውጣት እንደጀመረ ሞባይሉ ጮኸ..መጓዙን ሳያቆም አነሳው‹‹ሄሎ ዶክተር፡፡››
‹‹ሁሴን ሰላም ነህ?››
‹‹ሰላም ነኝ አንቺስ እንዴት ነሽ?››
‹‹ይመስገነው ሰሞኑን ትንሽ የስራ ውጥረት ስለነበረ ነው ላገኝህ ያልቻልኩት.. ዛሬ ከአስራአንድ ሰዓት በኃላ ነፃ ነኝ አንተን የሚመችህ ከሆነ…፡፡››
<<ችግር የለም ይመቸኛል..የት እንገናኝ፡፡››
‹‹ግዮን ቢሆን ይመቸኛል፡፡››
‹‹በቃ እዛው በሰዓቱ እደርሳለሁ፡፡››
‹‹እሺ አመሰግናለሁ ሁሴን፡፡››
‹‹እሺ ቻው ዶ/ር ሶፊያ››
ቤተሰቦች በቅናነት #YouTube #subscribe እያደረጋቹ በጣም ቀንሳችኋል 1ደቂቃ አይፈጅም ገብታችሁ #Subscribe አድርጉ አመሰግናለሁ።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍105❤8🔥1👏1
#ተገላቢጦሽ
ያኔ እኮ አብረሃም
ሲኖሮ በዚህ አለም
ሁሉ ተሟልቶለት
ምንም ሳይጎሎበት
ተናግሮ ነበረ
"ለዚች ትንሽ ጊዜ
ለ ስምንት መቶ አመት
ቤትማ አልቀልስም
ድንኳን መች አነሳት"
ዛሬ የሱ ዘሮች
ለሰማንያ አመት
ህንፃውን ገንብተው
ቤታቸውን ሰርተው
ሰፈሩንም አጥረው
ከድሀው ላይ ነጥቀው
.....ይጠባበቃሉ....
ከደጅ የቆመውን
ከዘጠኙ አንዱን፡፡
🎴ዘውዱ እርቅይሁን🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ያኔ እኮ አብረሃም
ሲኖሮ በዚህ አለም
ሁሉ ተሟልቶለት
ምንም ሳይጎሎበት
ተናግሮ ነበረ
"ለዚች ትንሽ ጊዜ
ለ ስምንት መቶ አመት
ቤትማ አልቀልስም
ድንኳን መች አነሳት"
ዛሬ የሱ ዘሮች
ለሰማንያ አመት
ህንፃውን ገንብተው
ቤታቸውን ሰርተው
ሰፈሩንም አጥረው
ከድሀው ላይ ነጥቀው
.....ይጠባበቃሉ....
ከደጅ የቆመውን
ከዘጠኙ አንዱን፡፡
🎴ዘውዱ እርቅይሁን🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍37❤7
#ዝምተኛ_ልቦች
አምነው የወደዱ
ወደው የተካዱ
ተክደው የራዱ
ፍርሃት አንሸራቶ ቁልቁል የጣላቸው
የብቸኛ ልቦች የትነው መውደቂያቸው?
የትነው መድረካቸው?
ማነው አጃቢያቸው?
እንዴት ነው ምታቸው
የተካዱ ልቦች አጋር የራቃቸው
የሚያቀነቅኑት ምንድን ነው ዜማቸው?
የተመረኮዙት እምነት ታጥፎባቸው
ድንገት የወደቁ ፍቅር ያዳጣቸው
ሚስጥር የሚያጋሩት ሰው የበደላቸው
ብቸኝነት ሰርጎ ብቻ ያስቀራቸው
ዝምተኛ ልቦች ምን ይሆን ቋንቋቸው?
ከየት ነው ጥሪያቸው?
በየት ነው ጉዟቸው?
የት ነው መድረሻቸው?
እንደ ሰብአሰገል ጠቅሶ የሚመራቸው
የቃተቱ ልቦች የታል ኮከባቸው?
መቼም ከአምላክ ትንፋሽ ከውሃ ከአፈሩ
ከእምንት እና እውነት ከፍቅር ሲሰሩ
ዝምተኛ ልቦች ጥንቱን ሲፈጥሩ
ተገፍትረው ወድቀው
ደቀው እንዳይቀሩ
በተስፋ ጸንተው ነው ዘላለም ሊኖሩ::
🎴ጌትነት እንየው🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
አምነው የወደዱ
ወደው የተካዱ
ተክደው የራዱ
ፍርሃት አንሸራቶ ቁልቁል የጣላቸው
የብቸኛ ልቦች የትነው መውደቂያቸው?
የትነው መድረካቸው?
ማነው አጃቢያቸው?
እንዴት ነው ምታቸው
የተካዱ ልቦች አጋር የራቃቸው
የሚያቀነቅኑት ምንድን ነው ዜማቸው?
የተመረኮዙት እምነት ታጥፎባቸው
ድንገት የወደቁ ፍቅር ያዳጣቸው
ሚስጥር የሚያጋሩት ሰው የበደላቸው
ብቸኝነት ሰርጎ ብቻ ያስቀራቸው
ዝምተኛ ልቦች ምን ይሆን ቋንቋቸው?
ከየት ነው ጥሪያቸው?
በየት ነው ጉዟቸው?
የት ነው መድረሻቸው?
እንደ ሰብአሰገል ጠቅሶ የሚመራቸው
የቃተቱ ልቦች የታል ኮከባቸው?
መቼም ከአምላክ ትንፋሽ ከውሃ ከአፈሩ
ከእምንት እና እውነት ከፍቅር ሲሰሩ
ዝምተኛ ልቦች ጥንቱን ሲፈጥሩ
ተገፍትረው ወድቀው
ደቀው እንዳይቀሩ
በተስፋ ጸንተው ነው ዘላለም ሊኖሩ::
🎴ጌትነት እንየው🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍40👏6🥰3
እባክሽ አትሂጂ…..
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-13
…
‹‹ያልገባኝ ከስምንት ወንዶች መካከል የተወለድሽ ብቸኛ ሴት ሆነሽ ሳለ እንዴት በአያትሽ እጅ አደግሽ...?ወላጆችሽ እንዴት እሺ ብለው ሰጡሽ ...?››ስል ጠየቅኳት
‹‹እሱ የራሱ የሆነ መራር ታሪክ አለው።ከእኔ በፊት ወላጆቼ ሁለት ሴት ልጆችን ወልደው ነበር፡፡ግን በተወለድ በአንድ ወራቸው ሁለቱም ሞቱ።ከዛ እኔ እንደተወለድኩ አያቴ በሶስተኛው ቀን ከእናቴ እቅፍ ነጠቀችና ወሰደችኝ።ከዛ የራሷን ደረቅ ጡት እያጠባች አሳደገቺኝ።በወቅቱ ወላጆቼ እኔን እንደሌሎቹ ትሞትብናለች የሚል ጥርጣሬ ስለነበራቸው ጨከን ብለው ተይ አትውሰጂያት ማለት አልቻሉም ነበር...በዛ ላይ አያቴ በጣም ተፈሪ ሰው ነበረች።››
‹‹የሚገርም ታሪክ ነው››አልኳት።
እኔ ቢራዬን እየደጋገምኩ እሷ ኮካዋን በዝግታ እየተጎነጨች ጫወታችንን ቀጠልን።
‹‹ግን እምቢ አልሽ እንጂ ወይን ነገር ብትሞክሪ ደስ ይለኝ ነበር፡፡››
‹‹ውይ ዶ/ር ግድ የለህም ይቅርብኝ።››
ሲያንቀዠቅዠኝ‹‹ለምንድነው ግን? ስለማትወጂ ነው?››ስል ጠየቅኳት።
‹‹አይ እንደውም በጣም ነው የምወደው..ግን እኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ወይን እንድቀምስ ያደረገኝ መስፍኔ ነው...ብዙ ጊዜም እጠጣ የነበረው ከእሱ ጋር ነው።እና አሁን እሱ እዛ አልጋ ላይ ተሰትሮ ለነፍሱ ሲታገል .እኔ እዚህ ወይን ልጠጣ ብሞክር ከጉሮሮዬ አይወርድልኝም።››ብላ አስገረመችኝ።ከዛ በምን ሞራሌ ካልጠጣሽ ብዬ ልጫናት እችለው…?የማይሆነውን፡፡.
እኔ በሀሳብ ሰምጬ ስለእሷ እና ባለቤቷ በማሰላሰል ላይ ሳለሁ በመሀል ድምፃን ሰማሁና ከሀሳብ ባነንኩ
‹‹ዶ/ር ለሁለት ነገር ነበር እፈልግሻለሁ ያልከኝ..እንዱን ሰማሁት በጣም ተደስቼያለሁ፡፡ ግን ሁለተኛው ምንድነው?››
ግራ ገባኝ ‹‹የምን ሁለተኛ?››
‹‹እንዴ ዘነጋኸው እንዴ? ለሁለት ነገር ነበር እፈልግሻለሁ ያልከኝ፡፡››
‹‹እ አዎ…ሁለተኛውማ ስለአንቺና መስፍን የፍቅር ታሪክ በቀደም ጀመረሺልኝ ልጆቹ ሲመጡ አቋረጥነው..እና እከዛሬ ሆዴን እንደቆረጠኝ ነው..እባክሽ አሁንእሱን እንድትነግረኝ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹እንዴ.ዶ/ር አሁን?››
‹‹አዎ..አሁን..››
‹‹ሞባይሏን አነሳችና አየች….ቢበዛ 30 ደቂቃ ብቻ ነው መቆየት የምችለው…መስፍኔ ለረጂም ጊዜ ሲያጣኝ ይሳቀቃል፡››
‹‹ገባኝ…በ30 ደቂቃ የቻልሺውን ያህል ንገሪኝና… ቀሪውን ደግሞ ወደሌላ ቀን እናስተላልፈዋልን፡፡››
‹‹እሺ ካልክ ..ግን ምን ላይ ነበር ያቆምኩልህ…››ለማስተዋስ መጣር ጀመረች፡፡
‹‹ እያበጠርሽ የነበረውን ፀጉርሽን እንዳንጨፈረርሽ የሚከራየውን ቤት ልታሳይው ወደክፍሎቹ እየመራሽ ስትወስጂው ነበር ያቆምሺው፡፡
‹‹አንተ..ጥሩ አድማጭ ነህ፡፡››
‹‹አይ ..ያን ያህል እንኳን አይደለሁም ..››
‹‹እንግዲህ እንዳልኩህ ፊት ለፊት እየመራው ወደክፍሎቹ ይዤው ሄድኩ፡፡ክፍሎቹ አንድ አንድ ስርቢስ ክፍል ናቸው፡፡ገብቶ ዞር ዞር እያለ አየውና‹‹ቀጣዩም ክፍል ተመሳሳይ ነው?››ሲል ጠየቀኝ፡፡
በራፍ ላይ እንደቆምኩ‹‹አዎ…ከፈለክ ልክፈትልህና እየው፡፡››አልኩት፡፡
‹‹አይ ተመሳሳይ ከሆነ ይቅርብኝ››
ድንግጥ አልኩ‹‹ምነው አልተመቸህም?አልኩት ››
‹‹አይ ተመሳሳይ ከሆነ ያኛውን ማየቱ አስፈላጊ አይደለም እያልኩሽ ነው››
ተንፈስ አልኩና‹‹እ እንደዛ ነው፡፡››
‹‹አዎ..ግን ስታስቢው የሚሆነኝ ይምስልሻል?››
‹‹አዎ በደንብ ይሆንሀል››አልኩት፡፡
ፍጥጥ ብሎ አየኝና ‹‹እንዴ !የምርሽን ነው?››ሲል ጠየቀኝ፡፡
‹‹አዎ እውነቴን ነው....ቀለሙንም ተላልጦል ካልክ ዛሬውኑ አስቀባልሀለው፡፡››
‹‹እሺ ስፋቱስ?››
‹‹ስፋቱ ይበቃሀል..ሰፊ እኮነው…ለአንድ ሰው ይሄ በጣም በቂ ነው፡፡››
‹‹አንድ ሰው ብቻ እንደሆንኩ በምን አወቅሽ..ሚስት የለኝም ብዬሻለሁ እንዴ?››ብሎ አሳፈረኝም አስደነገጠኝም፡፡
በኩርፊያ መልክ‹‹አይ ሚስት ያለህ ስላልመሰለኝ ነው..ሚስት ካለህ እንኳን ይቅርብህ …ይጠብሀል››አልኩት፡፡
‹‹እሺ ለመሀኑ ኪራዩ ስንት ነው?››
‹‹ሚስት ካለህ ሁለት ሺ ብር..››
ከት ብሎ ሰሳቀና ‹‹እሺ ሚስት ከሌለኝሽ….?››
‹‹ሚስት ከሌለህ ችግር የለውም የፈለከውን መክፈል ትችላለህ፡፡››
‹‹ወደኪሱ ገባና የሆኑ ብሮች አወጣና ቆጠር ቆጠር አድርጎ ከላዩ ላይ አምስት መቶ ብር አጄ ላይ አስቀመጠና‹‹ይሄ ቀብድ ነው.. በቃ ከዛሬ ጀምሮ ይሄንን ክፍል ተከራይቼዋለው…የዛሬ ሳምንት አካባቢ ገባበታለሁ…አሁን ወደጊቢሽ እንዳስገባሺኝ መልሰሽ አስወጪኝ››አለና ክፍሉን ለቆ በመውጣት እንደአመጣጡ ወደውጭ መራመድ ጀመረ ፡፡እኔም ከኃላው ግራ በመጋባት እከተለው ጀመር…››
‹‹ቆይ ግን ከሚስትህ ጋር ነው የምትገባው?››
‹‹እሱን ማወቅ ምን የደረግልሻል..?ሚስቴን ይዤ ከመጣው 2 ሺ ብር ከፍልሻለሁ…እሷን ፈትቼ ብቻዬን ከገባሁ ግን አንድ ሺ ብር ብቻ ነው የምከፍለው››
‹‹እሺ፡፡››
የውጭ በራፉ ጋር እንደደረስን ወደእኔ ዞሮ ትኩር ብሎ በፈገግታ እያየኝ፡፡‹‹ላንቺ ስል ግን ሚስቴን ይዤ ለመምጣት እሞክራለው፡፡››አለኝ፡፡
አበሳጨኝ‹‹እንዴ ሚስትህ ለእኔ ምን ትሰራልኛለች?››
‹‹ብዙ ነገር..አንደኛ እንዳንቺ በጣም ቆንጆ ስለሆነች ጓደኛ ትሆንሻለች…ሁለተኛ ጥሩ የኪራይ ገንዘብ ታገኚያለሽ፡፡››
‹‹አልፈልግም፡፡››
‹‹ምኑ ነው የማትፈልጊው .?.ከሚስቴ ጋር ጓደኛ መሆኑን ወይስ የኪራዩን ብር..?››
‹‹ሁለቱንም…፡፡››
አይኖቹን ከእኔ አሻግሮ ወደውስጥ ተመለከተና ከኃላችን ሰው እንደሌላ ካረጋገጠ በኃላ
‹‹በይ እስከሳምንት ትናፍቂኛለሽ… ደህና ሁኚ ›› ብሎ ጎንበስ በማለት ጉንጬን ሳመኝና ሌላ ምንም ሳይናገር ፊቱን ዞሮ ሄደ፡፡እኔ ግን እጄን ከንፈሩ ያረፈበትን የጉንጬን አካባቢ በፍቅርና በስስት እየዳበስኩ ድንዝዝ ብዬ ለበርካታ ደቂቃዎች ቆምኩ…ከንፈሩ ጉንጬ ላይ ሲያርፍ ልቤ ላይ ነው የሞቀኝ…አእምሮዬን ነው የነዘረኝ…፡፡.
ከዛ ሳምንቱ እንዴት ይለቅ..?ፍፅም ከዛ በፊት ሆኜ የማለቀውን አይነት ሰው ነው የሆንኩት…በአየር ላይ ስንሳፈፍ ከረምኩ..ሚስቱን ይዟት ይመጣ ይሆን…?እውነት እንደእኔ ቆንጆ ነች…?ደግሞ እንደአንቺ ቆንጆ ነች ካለ እኮ የእኔን ቆንጆነት ያምንበታል፡፡ግን ሚስት እያለው ለምን ሳመኝ..?ለምንስ ትናፍቂኛለሽ አለኝ….?በሳምንት ውስጥ ሳባት ኪሎ ያህል ሳልቀንስ አልቀርም፡፡ደግሞ ትክክለኛ የሚመጣበትን ቀንና ሰዓት አልነገረኝም ያም ሌላ ስቃይ ነበር የሆነብኝ፡፡በስምንተኛው ቀን በእለተ እሁድ በአንድ ፒካፕ መኪና አልጋ ፍራሽና የተወሰኑ የቤት እቃዎች ጭኖ ከች አለ፡፡ሮጬ ልጠመጠምበትና አገላብጬ ጉንጮችን ልስማቸው ፈልጌ ነበር፡፡ግን እንደዛ ማድረግ አልቻልኩም፡፡እሱም ሰላም እንኳን አላለኝም..በራፍን እንደከፈትኩላቸው መኪናዋ ወደውስጥ ገብታ እንደቆመች ከገቢናው ወርዶ ወደእኔ እየተመለከተ ያለኝ የመጀመሪያ ነገር ቢኖር…‹‹እቤቴ ቁልፍ ነው ወይስ ክፍት?›› ነበር፡፡
ዝም አልኩት..ክፍት ይሆን ቁልፍ ማስታወስ እንኳን ከበደኝ፡፡
እኔን ተወኝና ከላይ የነበረውን ፍራሹን ይዞ ወደጓሮ ሄደ ፡፡እዛው በረንዳ ላይ ደንዝዤ እንደቆምኩ ነው፡፡ ከሹፌሩ ጋር ተጋግዘው ዕቃውን አጓጉዘው ለመጨረስ15 ደቂቃም የፈጀባቸው አይመስለኝም፡፡ከዛ ወደእኔ ጠጋ አለና ‹‹አያትሽ አሉ..ፈልጌቸው ነበር፡፡››አለኝ፡፡
‹‹የለችም..ቤተክርስቲያን ነች፡፡››
‹‹በቃ..ቁልፍ ካለሽ ቤቱን ቆልፊልኝ››ብሎኝ ብቻ ፊቱን አዞረ፡፡
‹‹ልትሄድ ነው?››
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-13
…
‹‹ያልገባኝ ከስምንት ወንዶች መካከል የተወለድሽ ብቸኛ ሴት ሆነሽ ሳለ እንዴት በአያትሽ እጅ አደግሽ...?ወላጆችሽ እንዴት እሺ ብለው ሰጡሽ ...?››ስል ጠየቅኳት
‹‹እሱ የራሱ የሆነ መራር ታሪክ አለው።ከእኔ በፊት ወላጆቼ ሁለት ሴት ልጆችን ወልደው ነበር፡፡ግን በተወለድ በአንድ ወራቸው ሁለቱም ሞቱ።ከዛ እኔ እንደተወለድኩ አያቴ በሶስተኛው ቀን ከእናቴ እቅፍ ነጠቀችና ወሰደችኝ።ከዛ የራሷን ደረቅ ጡት እያጠባች አሳደገቺኝ።በወቅቱ ወላጆቼ እኔን እንደሌሎቹ ትሞትብናለች የሚል ጥርጣሬ ስለነበራቸው ጨከን ብለው ተይ አትውሰጂያት ማለት አልቻሉም ነበር...በዛ ላይ አያቴ በጣም ተፈሪ ሰው ነበረች።››
‹‹የሚገርም ታሪክ ነው››አልኳት።
እኔ ቢራዬን እየደጋገምኩ እሷ ኮካዋን በዝግታ እየተጎነጨች ጫወታችንን ቀጠልን።
‹‹ግን እምቢ አልሽ እንጂ ወይን ነገር ብትሞክሪ ደስ ይለኝ ነበር፡፡››
‹‹ውይ ዶ/ር ግድ የለህም ይቅርብኝ።››
ሲያንቀዠቅዠኝ‹‹ለምንድነው ግን? ስለማትወጂ ነው?››ስል ጠየቅኳት።
‹‹አይ እንደውም በጣም ነው የምወደው..ግን እኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ወይን እንድቀምስ ያደረገኝ መስፍኔ ነው...ብዙ ጊዜም እጠጣ የነበረው ከእሱ ጋር ነው።እና አሁን እሱ እዛ አልጋ ላይ ተሰትሮ ለነፍሱ ሲታገል .እኔ እዚህ ወይን ልጠጣ ብሞክር ከጉሮሮዬ አይወርድልኝም።››ብላ አስገረመችኝ።ከዛ በምን ሞራሌ ካልጠጣሽ ብዬ ልጫናት እችለው…?የማይሆነውን፡፡.
እኔ በሀሳብ ሰምጬ ስለእሷ እና ባለቤቷ በማሰላሰል ላይ ሳለሁ በመሀል ድምፃን ሰማሁና ከሀሳብ ባነንኩ
‹‹ዶ/ር ለሁለት ነገር ነበር እፈልግሻለሁ ያልከኝ..እንዱን ሰማሁት በጣም ተደስቼያለሁ፡፡ ግን ሁለተኛው ምንድነው?››
ግራ ገባኝ ‹‹የምን ሁለተኛ?››
‹‹እንዴ ዘነጋኸው እንዴ? ለሁለት ነገር ነበር እፈልግሻለሁ ያልከኝ፡፡››
‹‹እ አዎ…ሁለተኛውማ ስለአንቺና መስፍን የፍቅር ታሪክ በቀደም ጀመረሺልኝ ልጆቹ ሲመጡ አቋረጥነው..እና እከዛሬ ሆዴን እንደቆረጠኝ ነው..እባክሽ አሁንእሱን እንድትነግረኝ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹እንዴ.ዶ/ር አሁን?››
‹‹አዎ..አሁን..››
‹‹ሞባይሏን አነሳችና አየች….ቢበዛ 30 ደቂቃ ብቻ ነው መቆየት የምችለው…መስፍኔ ለረጂም ጊዜ ሲያጣኝ ይሳቀቃል፡››
‹‹ገባኝ…በ30 ደቂቃ የቻልሺውን ያህል ንገሪኝና… ቀሪውን ደግሞ ወደሌላ ቀን እናስተላልፈዋልን፡፡››
‹‹እሺ ካልክ ..ግን ምን ላይ ነበር ያቆምኩልህ…››ለማስተዋስ መጣር ጀመረች፡፡
‹‹ እያበጠርሽ የነበረውን ፀጉርሽን እንዳንጨፈረርሽ የሚከራየውን ቤት ልታሳይው ወደክፍሎቹ እየመራሽ ስትወስጂው ነበር ያቆምሺው፡፡
‹‹አንተ..ጥሩ አድማጭ ነህ፡፡››
‹‹አይ ..ያን ያህል እንኳን አይደለሁም ..››
‹‹እንግዲህ እንዳልኩህ ፊት ለፊት እየመራው ወደክፍሎቹ ይዤው ሄድኩ፡፡ክፍሎቹ አንድ አንድ ስርቢስ ክፍል ናቸው፡፡ገብቶ ዞር ዞር እያለ አየውና‹‹ቀጣዩም ክፍል ተመሳሳይ ነው?››ሲል ጠየቀኝ፡፡
በራፍ ላይ እንደቆምኩ‹‹አዎ…ከፈለክ ልክፈትልህና እየው፡፡››አልኩት፡፡
‹‹አይ ተመሳሳይ ከሆነ ይቅርብኝ››
ድንግጥ አልኩ‹‹ምነው አልተመቸህም?አልኩት ››
‹‹አይ ተመሳሳይ ከሆነ ያኛውን ማየቱ አስፈላጊ አይደለም እያልኩሽ ነው››
ተንፈስ አልኩና‹‹እ እንደዛ ነው፡፡››
‹‹አዎ..ግን ስታስቢው የሚሆነኝ ይምስልሻል?››
‹‹አዎ በደንብ ይሆንሀል››አልኩት፡፡
ፍጥጥ ብሎ አየኝና ‹‹እንዴ !የምርሽን ነው?››ሲል ጠየቀኝ፡፡
‹‹አዎ እውነቴን ነው....ቀለሙንም ተላልጦል ካልክ ዛሬውኑ አስቀባልሀለው፡፡››
‹‹እሺ ስፋቱስ?››
‹‹ስፋቱ ይበቃሀል..ሰፊ እኮነው…ለአንድ ሰው ይሄ በጣም በቂ ነው፡፡››
‹‹አንድ ሰው ብቻ እንደሆንኩ በምን አወቅሽ..ሚስት የለኝም ብዬሻለሁ እንዴ?››ብሎ አሳፈረኝም አስደነገጠኝም፡፡
በኩርፊያ መልክ‹‹አይ ሚስት ያለህ ስላልመሰለኝ ነው..ሚስት ካለህ እንኳን ይቅርብህ …ይጠብሀል››አልኩት፡፡
‹‹እሺ ለመሀኑ ኪራዩ ስንት ነው?››
‹‹ሚስት ካለህ ሁለት ሺ ብር..››
ከት ብሎ ሰሳቀና ‹‹እሺ ሚስት ከሌለኝሽ….?››
‹‹ሚስት ከሌለህ ችግር የለውም የፈለከውን መክፈል ትችላለህ፡፡››
‹‹ወደኪሱ ገባና የሆኑ ብሮች አወጣና ቆጠር ቆጠር አድርጎ ከላዩ ላይ አምስት መቶ ብር አጄ ላይ አስቀመጠና‹‹ይሄ ቀብድ ነው.. በቃ ከዛሬ ጀምሮ ይሄንን ክፍል ተከራይቼዋለው…የዛሬ ሳምንት አካባቢ ገባበታለሁ…አሁን ወደጊቢሽ እንዳስገባሺኝ መልሰሽ አስወጪኝ››አለና ክፍሉን ለቆ በመውጣት እንደአመጣጡ ወደውጭ መራመድ ጀመረ ፡፡እኔም ከኃላው ግራ በመጋባት እከተለው ጀመር…››
‹‹ቆይ ግን ከሚስትህ ጋር ነው የምትገባው?››
‹‹እሱን ማወቅ ምን የደረግልሻል..?ሚስቴን ይዤ ከመጣው 2 ሺ ብር ከፍልሻለሁ…እሷን ፈትቼ ብቻዬን ከገባሁ ግን አንድ ሺ ብር ብቻ ነው የምከፍለው››
‹‹እሺ፡፡››
የውጭ በራፉ ጋር እንደደረስን ወደእኔ ዞሮ ትኩር ብሎ በፈገግታ እያየኝ፡፡‹‹ላንቺ ስል ግን ሚስቴን ይዤ ለመምጣት እሞክራለው፡፡››አለኝ፡፡
አበሳጨኝ‹‹እንዴ ሚስትህ ለእኔ ምን ትሰራልኛለች?››
‹‹ብዙ ነገር..አንደኛ እንዳንቺ በጣም ቆንጆ ስለሆነች ጓደኛ ትሆንሻለች…ሁለተኛ ጥሩ የኪራይ ገንዘብ ታገኚያለሽ፡፡››
‹‹አልፈልግም፡፡››
‹‹ምኑ ነው የማትፈልጊው .?.ከሚስቴ ጋር ጓደኛ መሆኑን ወይስ የኪራዩን ብር..?››
‹‹ሁለቱንም…፡፡››
አይኖቹን ከእኔ አሻግሮ ወደውስጥ ተመለከተና ከኃላችን ሰው እንደሌላ ካረጋገጠ በኃላ
‹‹በይ እስከሳምንት ትናፍቂኛለሽ… ደህና ሁኚ ›› ብሎ ጎንበስ በማለት ጉንጬን ሳመኝና ሌላ ምንም ሳይናገር ፊቱን ዞሮ ሄደ፡፡እኔ ግን እጄን ከንፈሩ ያረፈበትን የጉንጬን አካባቢ በፍቅርና በስስት እየዳበስኩ ድንዝዝ ብዬ ለበርካታ ደቂቃዎች ቆምኩ…ከንፈሩ ጉንጬ ላይ ሲያርፍ ልቤ ላይ ነው የሞቀኝ…አእምሮዬን ነው የነዘረኝ…፡፡.
ከዛ ሳምንቱ እንዴት ይለቅ..?ፍፅም ከዛ በፊት ሆኜ የማለቀውን አይነት ሰው ነው የሆንኩት…በአየር ላይ ስንሳፈፍ ከረምኩ..ሚስቱን ይዟት ይመጣ ይሆን…?እውነት እንደእኔ ቆንጆ ነች…?ደግሞ እንደአንቺ ቆንጆ ነች ካለ እኮ የእኔን ቆንጆነት ያምንበታል፡፡ግን ሚስት እያለው ለምን ሳመኝ..?ለምንስ ትናፍቂኛለሽ አለኝ….?በሳምንት ውስጥ ሳባት ኪሎ ያህል ሳልቀንስ አልቀርም፡፡ደግሞ ትክክለኛ የሚመጣበትን ቀንና ሰዓት አልነገረኝም ያም ሌላ ስቃይ ነበር የሆነብኝ፡፡በስምንተኛው ቀን በእለተ እሁድ በአንድ ፒካፕ መኪና አልጋ ፍራሽና የተወሰኑ የቤት እቃዎች ጭኖ ከች አለ፡፡ሮጬ ልጠመጠምበትና አገላብጬ ጉንጮችን ልስማቸው ፈልጌ ነበር፡፡ግን እንደዛ ማድረግ አልቻልኩም፡፡እሱም ሰላም እንኳን አላለኝም..በራፍን እንደከፈትኩላቸው መኪናዋ ወደውስጥ ገብታ እንደቆመች ከገቢናው ወርዶ ወደእኔ እየተመለከተ ያለኝ የመጀመሪያ ነገር ቢኖር…‹‹እቤቴ ቁልፍ ነው ወይስ ክፍት?›› ነበር፡፡
ዝም አልኩት..ክፍት ይሆን ቁልፍ ማስታወስ እንኳን ከበደኝ፡፡
እኔን ተወኝና ከላይ የነበረውን ፍራሹን ይዞ ወደጓሮ ሄደ ፡፡እዛው በረንዳ ላይ ደንዝዤ እንደቆምኩ ነው፡፡ ከሹፌሩ ጋር ተጋግዘው ዕቃውን አጓጉዘው ለመጨረስ15 ደቂቃም የፈጀባቸው አይመስለኝም፡፡ከዛ ወደእኔ ጠጋ አለና ‹‹አያትሽ አሉ..ፈልጌቸው ነበር፡፡››አለኝ፡፡
‹‹የለችም..ቤተክርስቲያን ነች፡፡››
‹‹በቃ..ቁልፍ ካለሽ ቤቱን ቆልፊልኝ››ብሎኝ ብቻ ፊቱን አዞረ፡፡
‹‹ልትሄድ ነው?››
👍57❤7🤔2👏1
‹‹አዎ..ሚስቴ ያቺን የመሰለች ቆንጆ ልጅ ያለችበት ግቢ አልገባም ብላ እያስቸገረችኝ ነው… አሁን እሷን ልለምን እየሄድኩ ነው፡፡እሺ ካለቺኝ ጥሩ ..እምቢ ካለችኝ ግን ይሄ የሆነው በአንቺ ምክንያት ስለሆነ ተመልሼ አንቺኑ ነው የማገባው››ብሎኝ እርምጃውን አፈጠነና መኪና ውስጥ ገብቶ ወጥቶ ሄደ…፡፡
ብላ ከመቀመጫዋ ተነሳች፡፡እኔ በድንዛዜና በተመስጦ እያዳመጥኳት ነበርና፤ በመነሳቷ ግራ ተጋባሁ‹‹ምነው…?››
‹‹.ሰላሳ ደቂቃው አለፈ…ወደቤት ልሄድ..ቀጣዩን ደግሞ ሰሞኑን ነግርሀለው››አለችኝ፡፡
‹‹ልክ እሱ አድርጎሽ እንደነበረው አሁንም አንቺ እኔን እያደረግሽ ነው››ስል አልጎመጎምኩ፡፡
‹‹አይ ዶ/ር..የእሱማ ከምንም አይገጥም ….ጮርቃውን ወጣትነቴን እና የዋህ አፍቃሪነቴን ገና በመጀመሪያው ቀን ተረድቶ ተጫወተብኛል…በል ቸው፡፡››
በዛው ተለያየን፡፡ቀጥታ ወደእማዬ ቤት አመራሁ…..ደግሞ እዛ ምን ይገጥመኝ ይሆን..እርግበ አሁንም እዛ ትሆን ወይስ ወደዘመዶቾ ሄዳለች?
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
ብላ ከመቀመጫዋ ተነሳች፡፡እኔ በድንዛዜና በተመስጦ እያዳመጥኳት ነበርና፤ በመነሳቷ ግራ ተጋባሁ‹‹ምነው…?››
‹‹.ሰላሳ ደቂቃው አለፈ…ወደቤት ልሄድ..ቀጣዩን ደግሞ ሰሞኑን ነግርሀለው››አለችኝ፡፡
‹‹ልክ እሱ አድርጎሽ እንደነበረው አሁንም አንቺ እኔን እያደረግሽ ነው››ስል አልጎመጎምኩ፡፡
‹‹አይ ዶ/ር..የእሱማ ከምንም አይገጥም ….ጮርቃውን ወጣትነቴን እና የዋህ አፍቃሪነቴን ገና በመጀመሪያው ቀን ተረድቶ ተጫወተብኛል…በል ቸው፡፡››
በዛው ተለያየን፡፡ቀጥታ ወደእማዬ ቤት አመራሁ…..ደግሞ እዛ ምን ይገጥመኝ ይሆን..እርግበ አሁንም እዛ ትሆን ወይስ ወደዘመዶቾ ሄዳለች?
ይቀጥላል...
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
❤15👍15
💥💞#አልተዘዋወረችም💥💞
✍ አሌክስ አብርሃም
ክፍል አስራ ሰባት
“እያንዳንዱ ጓደኝነት ውስጥ ትንሽ ትንሽ ጠላትነት አለ!”
ሃይማኖት!
እንደ እኔ መልኳ ብዙም ለማይስብ ሴት፣ ጥሩ አፍቃሪ ማግኜት ከረዥም ዛፍ ላይ በአጭር ቁመት ፍሬ ለማውረድ እንደመሞከር ነው “ሴትነት” ብቻውን በቂ አይደለም፤ ፍሬውን ማውረጃ አንዳች ዘንግ ያስፈልጋል፡፡ ፍሬው ላይ የሚደርስ የትምህርት ፣ የገንዘብ ፣ የጥሩ ምላስ፣ ባለቤት መሆን ያስፈልጋል፤ አልያም ቁመትን የሚያረዝም የጥሩ ቤተሰብ መሰላል ላይ መቆም፡፡ ይኼን ዘንግ በእጄ እስክጨብጥ ስንቱ ያስጎመጄኝ ፍሬ የወፍ ሲሳይ ሆነ፡፡ ተስፋ አስቆራጭ መልክ ነው ያለኝ፡፡ በዚያ ብኩለው በዚህ አስቀያሚነቱ እየባሰበት የሚሄድ፡፡ ምንሽ ነው የሚያስጠላው? ቢሉኝ አላውቅም፤ ግን እንዲሁ መልኬ ቆሜ እያዩኝ እዚያው በቆምኩበት የሚረሳ ዓይነት ነው፡፡ ሰው ካልታወሰ ምኑ ይፈቀራል? የመፈቀር ተቃራኒው መጠላት አይደለም፤ መረሳት ነው፡፡ ማንም የሚያፈቅረውን አይረሳም፤ እኔ ግን ሰዎች አእምሮ ውስጥ በትዝታ መዝገብ እንዳልጻፍ የተረገምኩ ይመስለኛል፡፡ በዚህ እና በሌላ ሌላ ብዙ ምክንያቶች ስለ ራሴ ከማሰብ ይልቅ፣ ስለሌሎች ጉዳይ በማያገባኝ ገብቼ መፈትፈት እወዳለሁ፡፡ ሌሎች ላይ ለመድረስ ሳይሆን ከራሴ ለመሸሽ።
አብሮ አደግ ጓደኛዬ ማኅደረን ጨምሮ የሚቀርቡኝ ሁሉ “ለግጥምና ሥነ-ጽሑፍ ሟች ነሽ' ይሉኛል፣ አይደለሁም። የሚሞትለት ነገር ጠፋ እንዴ? እንዲያውም ግጥም የሚሉትን ነገር አልወድም፤ ምኑም አይጥመኝም፡፡ ግጥም በተለይ ረዥም ግጥም፣ የጅል ለቅሶ ይመስለኛል፡፡ አንዳንድ ገጣሚዎች በአቀራረባቼው እና ቀለል አድርገው በሚያነሱት ሀሳብ ያስቁኛል፣ ሳቅ ማን ይጠላል? በተለይ እኔ ሳቅ በሁለት ምክንያት እወዳለሁ...የመጀመሪያው ሳቅ ያው ሳቅ ስለሆነ ነው፣ ሁለተኛው ግን ጥርስሽ ያምራል ስለሚሉኝ ስስቅ እኩል ሁለት ደስታዎችን ስለማጣጥም ነው፤ በአንድ የሳቅ ጠጠር፣ ሁለት የደስታ ወፍ እንደማውረድ። የሆነ ሆኖ እንደዚያ ዓይነት ግጥሞችን፣ ፍቅረኛዬ ቶማስ ዝርው፣ተራ፣ ገለባ ናቸው ይላቼዋል፡፡ እሱ ራሱ ዝርው ተራና ገለባ የሆነ ልጅ ነበር፡፡ “ትንሽ ካላሳሰቡሽ ምኑን ግጥም ሆኑ?'' የሚለው ነገር አለ (ግድ ካላሰብኩ ብሎ ነገር!) አስበን የምንደርስበትን እዚያው አስበው ፍሬ ነገሩን ከነገሩን ምን አደከመን? ዘመናችን የጥድፊያ ነው፣ ቁጭ ብሎ ለመቆዘም ፋታ አይሰጥም። ሥራችን ነው ካሉ፣ እዚያው ቆዝመውም ይሁን ተጨንቀው፣ ሊሉን የፈለጉትን በአጭርና በግልጽ ቋንቋ ይንገሩን። ቢሆንም ፍቅረኛዬ ቶማስ የተመረቀው በሥነ-ጽሑፍ ምናምን ነውና በዚህ ጉዳይ ገፍቼ አልከራከረውም፡፡ ለነገሩ በምንም ጉዳይ አልከራከረውም። ቶማስ ውስጡ የተቀበረ ቁጭት አለበት፣ ሰዎች ሲጨበጨብላቼው ይበሳጫል። አንዳንዴ ደግሞ ስም የሌለው ገጣሚ በታዋቂዎቹ መካከል ግጥም ሲያቀርብ እና ከተመልካቹ ቀዝቀዝ ያለ ጭብጨባ ሲቼረው፣ ቶማስ ረዢምና ደማቅ ጭብጨባ ያጨበጭባል፣ ሊቆም የሚያዘግመው ጭብጨባ እንደገና ነፍስ ይዘራል፡፡ ቶማስ ለታዋቂ ገጣሚያን ጥላቻ እንዳለበት እረዳለሁ። ገጣሚያን ብቻ ሳይሆን ማንኛውም ታዋቂ ሰው ያበሳጨዋል፤ በተለይ ኢትዮጵያዊ፣ ግን ለምን ብዬ አልጠይቀውም ነበር፡፡ ብዙ ጊዜ ግጥም እንደሚጽፍ ቢነግረኝም፣ በሦስት ዓመት ቆይታችን አንድም _ መስመር ጽፎ ዓይቼ አላውቅም፡፡ _ አይደለምና / ግጥም፣ መደበኛውን መጻፍና ማንበብ መቻሉ እስኪያጠራጥረኝ፣ እጁ ላይ ብዕርም መጽሐፍም ዓይቼ አላውቅም፤ ግድ አይሰጠኝም፡፡
ቶማስ ጋር እንዴት ፍቅረኞች ሆንን? በፍቅሩ ወድቄ ነው? አይደለም፡፡ ፍቅረኛ የሆንበት ብቼኛ ምክንያት ታክሲ ውስጥ ገብቼ ጎኑ ስቀመጥ ገና በወጉ እንኳን ተደላድዬ ሳልቀመጥ “ኦህ! ጥርስሽ እንዴት ያምራል!'' ስላለኝ ብቻ ነው፡፡ ዞር ብዬ አዬሁት፣ ብጉራም ነው እንጂ መልኩ ደህና ነው “አመሰግናለሁ” ብዬ ልዘጋው እቺል ነበር፡፡ ግን በሕይወቴ እንደ ፀሐይ ግርዶሽ በስንት አንድ ጊዜ ያውም ከማያውቀኝ ወንድ የሚሰነዘር አድናቆት እንደ ተራ ነገር ማለፍ የምችል ልጅ አልነበርኩም። አድናቆት ያሳሳኛል፤ የሚያደንቁኝ ሰዎች ጻድቃን ነው የሚመስሉኝ፡፡ ፈገግ ብዬ፣ “ገና ከመግባቴ ...የት አዬኸው ጥርሴን?'' አልኩት፡፡ ይኼ ፈገግታዬ ድፍረት ሰጥቶት ወሬ ጀመርን፡፡ እና ልክ እንደፈላስፎች በቀልድ የሌለውን ፂም እየጎተተ “ታክሲ ውስጥ ከመግባትሽ በፊት ጓደኛሽ ጋር ስትሰነባበች ፈገግ ብለሽ አልነበረምን?'' አለ፡፡ የእውነት አሳቀኝ። እጁን ዘርግቶ “ቶማስ እባላለሁ' አለኝ፡፡ ጨበጥኩት፤ የሴት እጅ እንኳን እንደዚያ አይለሰልስም፡፡ የእጁ ልስላሴ የተለዬ ምቾት ይፈጥራል፡፡ እንዲህ ተዋወቅን፡፡ የዚያን ቀን ስልኬን ሲጠይቀኝ አልከለከልኩትም፤ ግን ይደውላል ብዬ አላስብኩም ነበር፡፡ ላግኝሽ ሲለኝ አልከለከልኩትም፣ግን ቀጥሮኝ ይቀራል ብዬ ፈርቼ ነበር። ልሳምሽ ሲለኝ አልከለከልኩትም፣ ልተኛሽ ሲለኝ አልከለከልኩትም...አብረን የተኛን ቀን አለቀሰ፡፡ እስካሁንም ያ ነገር አንጀቴን ይበላኛል፡፡ እዚህ የጡት ዘር ያልፈጠረበት ባዶ ደረቴ ላይ ተለጥፎ አለቀሰ፡፡ ምንም ነገር ከልክዬው አላውቅም፡፡ እንደማያፈቅረኝ አውቃለሁ፣ እኔም አላፈቅረውም ነበርና ግድ አልነበረኝም። ሥራ አልነበረውም፤ ሳውቀው ጀምሮ ሥራ አልነበረውም። ሥራ ሲፈልግም አይቼው አላውቅም፤ እሱም ያን ያኽል አሳስቦኝ አያውቅም፡፡ እንዲያውም የሻይ እያልኩ በየወሩ የተወሰነ ብር እሰጠው ነበር፡፡ ይኼ ነገር ውለታ ሆኖበት ይሁን ወይም ሌላ መሄጃ ስለሌለው እንጃ እስከ መጨረሻው ከእኔ ጋር ነበር፡፡
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሥነጽሑፍ ተመርቆ ለሦስት ዓመት ሥራ ሳያገኝ ቆይቷል፡፡ እንዴት እንደሚኖር ለራሴም ይገርመኛል፡፡ግን ጠይቄው አላውቅም፡፡ እየቆዬ ሲገባኝ እሱም ከእኔ በባሰ ሁኔታ የተገፋና በራስ መተማመኑ የተንኮታኮተ ልጅ ነበር፡፡ ልዩነታችን ይኼን መገፋታችንን የተቀበልንበት መንገድ ላይ ነበር፡፡ እኔ ወደ ውስጤ ኖርኩት፤ እሱ በጥላቻ፣ በጠብ፣ በማማረር እና ሌሎችን በማናናቅ ኖረው። መሠረታዊ ችግራችን ግን ያው መገፋት ነበር፡፡ ከጓደኛዬ ማኅደረ ሰላም ፍቅረኛ አብርሃም ውጭ ቶማስን የሚወደው ይቅርና አብሮት ለደቂቃዎች መቀመጥ የሚፈልግ አንድም ሰው አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡ የሰው ዘር በሙሉ ክንፍ ያለው መልአክ ነው ብላ ልትከራከር የሚቃጣት ጓደኛዬ ማኅደረ እንኳን ቶማስን አትወደውም ነበር፡፡ “አልፈሽ ልትወጂው ብትሞክሪ እንኳን ዙሪያውን በእሾህ አጥር የታጠረ ልጅ ነው፣ በዬት ሽንቁር አልፈሽ እንደወደድሽው እንጃልሽ'' ትለኛለች፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰው ጋር ነው የኖርኩት። “በፍቅር”፡፡ የሆነ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የሥነ-ጽሑፍ ዝግጅት ላይ እንደ ፍቅረኛ ክንዴን ይዞ የወሰደኝ ቶማስ ነበር። ለእኔ ይኼ ማለት ብዙ ነገር ነው፡፡ ለቅሶ ቤት ይውሰደኝ፣ ሰርግ ቤት ጉዳዬ አልነበረም፤ ሳያፍርብኝ እጄን ይዞ ሰው መኻል የሚገኝ ሰው ከጎኔ መኖሩ ብቻውን የሚሰጠኝ ስሜት የተለዬ ነበር። ከዚያ በኋላ ብዙ የሥነ-ጽሑፍና የግጥም ዝግጅቶች ላይ ቶማስ ጋርም ይሁን ብቻዬን እገኝ ነበር። እንዲሁ የግጥም ምሽቶች ላይ መገኜት የሆነ ዘመናዊነት ነገር አለው አይደል?! የሥዕል ኤግዝቢሽን፣ የሥነ-ጽሑፍ ምሽት ምናምን? በተለይ “ምሽት'' የሚለው ደስ ይላል። "Maslow's hierarchy of needs" እንደሚነግረን የሰው ልጅ የዕለት ጉርሱን የዓመት ልብሱን ካገኜ በኋላ ጥጋብና ብርዱን ከመከላከል ባለፈ የመታዬት፣ የመወደድ ፍላጎቱን ለማርካት ይታትራል። ምንም ደሃ አገር ብንኖር
✍ አሌክስ አብርሃም
ክፍል አስራ ሰባት
“እያንዳንዱ ጓደኝነት ውስጥ ትንሽ ትንሽ ጠላትነት አለ!”
ሃይማኖት!
እንደ እኔ መልኳ ብዙም ለማይስብ ሴት፣ ጥሩ አፍቃሪ ማግኜት ከረዥም ዛፍ ላይ በአጭር ቁመት ፍሬ ለማውረድ እንደመሞከር ነው “ሴትነት” ብቻውን በቂ አይደለም፤ ፍሬውን ማውረጃ አንዳች ዘንግ ያስፈልጋል፡፡ ፍሬው ላይ የሚደርስ የትምህርት ፣ የገንዘብ ፣ የጥሩ ምላስ፣ ባለቤት መሆን ያስፈልጋል፤ አልያም ቁመትን የሚያረዝም የጥሩ ቤተሰብ መሰላል ላይ መቆም፡፡ ይኼን ዘንግ በእጄ እስክጨብጥ ስንቱ ያስጎመጄኝ ፍሬ የወፍ ሲሳይ ሆነ፡፡ ተስፋ አስቆራጭ መልክ ነው ያለኝ፡፡ በዚያ ብኩለው በዚህ አስቀያሚነቱ እየባሰበት የሚሄድ፡፡ ምንሽ ነው የሚያስጠላው? ቢሉኝ አላውቅም፤ ግን እንዲሁ መልኬ ቆሜ እያዩኝ እዚያው በቆምኩበት የሚረሳ ዓይነት ነው፡፡ ሰው ካልታወሰ ምኑ ይፈቀራል? የመፈቀር ተቃራኒው መጠላት አይደለም፤ መረሳት ነው፡፡ ማንም የሚያፈቅረውን አይረሳም፤ እኔ ግን ሰዎች አእምሮ ውስጥ በትዝታ መዝገብ እንዳልጻፍ የተረገምኩ ይመስለኛል፡፡ በዚህ እና በሌላ ሌላ ብዙ ምክንያቶች ስለ ራሴ ከማሰብ ይልቅ፣ ስለሌሎች ጉዳይ በማያገባኝ ገብቼ መፈትፈት እወዳለሁ፡፡ ሌሎች ላይ ለመድረስ ሳይሆን ከራሴ ለመሸሽ።
አብሮ አደግ ጓደኛዬ ማኅደረን ጨምሮ የሚቀርቡኝ ሁሉ “ለግጥምና ሥነ-ጽሑፍ ሟች ነሽ' ይሉኛል፣ አይደለሁም። የሚሞትለት ነገር ጠፋ እንዴ? እንዲያውም ግጥም የሚሉትን ነገር አልወድም፤ ምኑም አይጥመኝም፡፡ ግጥም በተለይ ረዥም ግጥም፣ የጅል ለቅሶ ይመስለኛል፡፡ አንዳንድ ገጣሚዎች በአቀራረባቼው እና ቀለል አድርገው በሚያነሱት ሀሳብ ያስቁኛል፣ ሳቅ ማን ይጠላል? በተለይ እኔ ሳቅ በሁለት ምክንያት እወዳለሁ...የመጀመሪያው ሳቅ ያው ሳቅ ስለሆነ ነው፣ ሁለተኛው ግን ጥርስሽ ያምራል ስለሚሉኝ ስስቅ እኩል ሁለት ደስታዎችን ስለማጣጥም ነው፤ በአንድ የሳቅ ጠጠር፣ ሁለት የደስታ ወፍ እንደማውረድ። የሆነ ሆኖ እንደዚያ ዓይነት ግጥሞችን፣ ፍቅረኛዬ ቶማስ ዝርው፣ተራ፣ ገለባ ናቸው ይላቼዋል፡፡ እሱ ራሱ ዝርው ተራና ገለባ የሆነ ልጅ ነበር፡፡ “ትንሽ ካላሳሰቡሽ ምኑን ግጥም ሆኑ?'' የሚለው ነገር አለ (ግድ ካላሰብኩ ብሎ ነገር!) አስበን የምንደርስበትን እዚያው አስበው ፍሬ ነገሩን ከነገሩን ምን አደከመን? ዘመናችን የጥድፊያ ነው፣ ቁጭ ብሎ ለመቆዘም ፋታ አይሰጥም። ሥራችን ነው ካሉ፣ እዚያው ቆዝመውም ይሁን ተጨንቀው፣ ሊሉን የፈለጉትን በአጭርና በግልጽ ቋንቋ ይንገሩን። ቢሆንም ፍቅረኛዬ ቶማስ የተመረቀው በሥነ-ጽሑፍ ምናምን ነውና በዚህ ጉዳይ ገፍቼ አልከራከረውም፡፡ ለነገሩ በምንም ጉዳይ አልከራከረውም። ቶማስ ውስጡ የተቀበረ ቁጭት አለበት፣ ሰዎች ሲጨበጨብላቼው ይበሳጫል። አንዳንዴ ደግሞ ስም የሌለው ገጣሚ በታዋቂዎቹ መካከል ግጥም ሲያቀርብ እና ከተመልካቹ ቀዝቀዝ ያለ ጭብጨባ ሲቼረው፣ ቶማስ ረዢምና ደማቅ ጭብጨባ ያጨበጭባል፣ ሊቆም የሚያዘግመው ጭብጨባ እንደገና ነፍስ ይዘራል፡፡ ቶማስ ለታዋቂ ገጣሚያን ጥላቻ እንዳለበት እረዳለሁ። ገጣሚያን ብቻ ሳይሆን ማንኛውም ታዋቂ ሰው ያበሳጨዋል፤ በተለይ ኢትዮጵያዊ፣ ግን ለምን ብዬ አልጠይቀውም ነበር፡፡ ብዙ ጊዜ ግጥም እንደሚጽፍ ቢነግረኝም፣ በሦስት ዓመት ቆይታችን አንድም _ መስመር ጽፎ ዓይቼ አላውቅም፡፡ _ አይደለምና / ግጥም፣ መደበኛውን መጻፍና ማንበብ መቻሉ እስኪያጠራጥረኝ፣ እጁ ላይ ብዕርም መጽሐፍም ዓይቼ አላውቅም፤ ግድ አይሰጠኝም፡፡
ቶማስ ጋር እንዴት ፍቅረኞች ሆንን? በፍቅሩ ወድቄ ነው? አይደለም፡፡ ፍቅረኛ የሆንበት ብቼኛ ምክንያት ታክሲ ውስጥ ገብቼ ጎኑ ስቀመጥ ገና በወጉ እንኳን ተደላድዬ ሳልቀመጥ “ኦህ! ጥርስሽ እንዴት ያምራል!'' ስላለኝ ብቻ ነው፡፡ ዞር ብዬ አዬሁት፣ ብጉራም ነው እንጂ መልኩ ደህና ነው “አመሰግናለሁ” ብዬ ልዘጋው እቺል ነበር፡፡ ግን በሕይወቴ እንደ ፀሐይ ግርዶሽ በስንት አንድ ጊዜ ያውም ከማያውቀኝ ወንድ የሚሰነዘር አድናቆት እንደ ተራ ነገር ማለፍ የምችል ልጅ አልነበርኩም። አድናቆት ያሳሳኛል፤ የሚያደንቁኝ ሰዎች ጻድቃን ነው የሚመስሉኝ፡፡ ፈገግ ብዬ፣ “ገና ከመግባቴ ...የት አዬኸው ጥርሴን?'' አልኩት፡፡ ይኼ ፈገግታዬ ድፍረት ሰጥቶት ወሬ ጀመርን፡፡ እና ልክ እንደፈላስፎች በቀልድ የሌለውን ፂም እየጎተተ “ታክሲ ውስጥ ከመግባትሽ በፊት ጓደኛሽ ጋር ስትሰነባበች ፈገግ ብለሽ አልነበረምን?'' አለ፡፡ የእውነት አሳቀኝ። እጁን ዘርግቶ “ቶማስ እባላለሁ' አለኝ፡፡ ጨበጥኩት፤ የሴት እጅ እንኳን እንደዚያ አይለሰልስም፡፡ የእጁ ልስላሴ የተለዬ ምቾት ይፈጥራል፡፡ እንዲህ ተዋወቅን፡፡ የዚያን ቀን ስልኬን ሲጠይቀኝ አልከለከልኩትም፤ ግን ይደውላል ብዬ አላስብኩም ነበር፡፡ ላግኝሽ ሲለኝ አልከለከልኩትም፣ግን ቀጥሮኝ ይቀራል ብዬ ፈርቼ ነበር። ልሳምሽ ሲለኝ አልከለከልኩትም፣ ልተኛሽ ሲለኝ አልከለከልኩትም...አብረን የተኛን ቀን አለቀሰ፡፡ እስካሁንም ያ ነገር አንጀቴን ይበላኛል፡፡ እዚህ የጡት ዘር ያልፈጠረበት ባዶ ደረቴ ላይ ተለጥፎ አለቀሰ፡፡ ምንም ነገር ከልክዬው አላውቅም፡፡ እንደማያፈቅረኝ አውቃለሁ፣ እኔም አላፈቅረውም ነበርና ግድ አልነበረኝም። ሥራ አልነበረውም፤ ሳውቀው ጀምሮ ሥራ አልነበረውም። ሥራ ሲፈልግም አይቼው አላውቅም፤ እሱም ያን ያኽል አሳስቦኝ አያውቅም፡፡ እንዲያውም የሻይ እያልኩ በየወሩ የተወሰነ ብር እሰጠው ነበር፡፡ ይኼ ነገር ውለታ ሆኖበት ይሁን ወይም ሌላ መሄጃ ስለሌለው እንጃ እስከ መጨረሻው ከእኔ ጋር ነበር፡፡
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሥነጽሑፍ ተመርቆ ለሦስት ዓመት ሥራ ሳያገኝ ቆይቷል፡፡ እንዴት እንደሚኖር ለራሴም ይገርመኛል፡፡ግን ጠይቄው አላውቅም፡፡ እየቆዬ ሲገባኝ እሱም ከእኔ በባሰ ሁኔታ የተገፋና በራስ መተማመኑ የተንኮታኮተ ልጅ ነበር፡፡ ልዩነታችን ይኼን መገፋታችንን የተቀበልንበት መንገድ ላይ ነበር፡፡ እኔ ወደ ውስጤ ኖርኩት፤ እሱ በጥላቻ፣ በጠብ፣ በማማረር እና ሌሎችን በማናናቅ ኖረው። መሠረታዊ ችግራችን ግን ያው መገፋት ነበር፡፡ ከጓደኛዬ ማኅደረ ሰላም ፍቅረኛ አብርሃም ውጭ ቶማስን የሚወደው ይቅርና አብሮት ለደቂቃዎች መቀመጥ የሚፈልግ አንድም ሰው አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡ የሰው ዘር በሙሉ ክንፍ ያለው መልአክ ነው ብላ ልትከራከር የሚቃጣት ጓደኛዬ ማኅደረ እንኳን ቶማስን አትወደውም ነበር፡፡ “አልፈሽ ልትወጂው ብትሞክሪ እንኳን ዙሪያውን በእሾህ አጥር የታጠረ ልጅ ነው፣ በዬት ሽንቁር አልፈሽ እንደወደድሽው እንጃልሽ'' ትለኛለች፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰው ጋር ነው የኖርኩት። “በፍቅር”፡፡ የሆነ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የሥነ-ጽሑፍ ዝግጅት ላይ እንደ ፍቅረኛ ክንዴን ይዞ የወሰደኝ ቶማስ ነበር። ለእኔ ይኼ ማለት ብዙ ነገር ነው፡፡ ለቅሶ ቤት ይውሰደኝ፣ ሰርግ ቤት ጉዳዬ አልነበረም፤ ሳያፍርብኝ እጄን ይዞ ሰው መኻል የሚገኝ ሰው ከጎኔ መኖሩ ብቻውን የሚሰጠኝ ስሜት የተለዬ ነበር። ከዚያ በኋላ ብዙ የሥነ-ጽሑፍና የግጥም ዝግጅቶች ላይ ቶማስ ጋርም ይሁን ብቻዬን እገኝ ነበር። እንዲሁ የግጥም ምሽቶች ላይ መገኜት የሆነ ዘመናዊነት ነገር አለው አይደል?! የሥዕል ኤግዝቢሽን፣ የሥነ-ጽሑፍ ምሽት ምናምን? በተለይ “ምሽት'' የሚለው ደስ ይላል። "Maslow's hierarchy of needs" እንደሚነግረን የሰው ልጅ የዕለት ጉርሱን የዓመት ልብሱን ካገኜ በኋላ ጥጋብና ብርዱን ከመከላከል ባለፈ የመታዬት፣ የመወደድ ፍላጎቱን ለማርካት ይታትራል። ምንም ደሃ አገር ብንኖር
👍41❤8
ያለችንን ለማሳዬት ጥምቀትን መጠበቅ የለብንም። መቼም እንዲህ እንዲህ ያሉት ቦታዎች እንይ ብሎ ለመታዬት የሚሄደው ባይበዛ ነው? ምኔ ነው ተረት ተረት? ምኔ ነው ግጥም? ምኔ ነው ሐሳብ? ጥበብ ቅብርጥስ...እነዚያ በቁማቼው ጫጭተው፣
የተላመጠ የወይራ መፋቂያ ከመሰሉ ገጣሚ ተብዬዎች ምን ጠብ ሊል?...ተጠበ ተጨንቆ ትልቅ ሥራ እንደሠራ ሰው ከመድረክ ወርደው ሲጋራቼውን በላይ በላዩ ሲያቦኑ እና መጠጣቼውን ሲገለብጡ ደሜ ይፈላል፡፡ በእርግጥ ከፍቅረኛዬ ቶማስ ይሻላሉ፤ እሱ እንዲሁ በመቆዘም ብቻ፤ ደክሞ የሚውልና የሚያድር ድብርታም ነበር። ሲጋራና መጠጡም አይቀርበት፡፡ አንድም ቀን ይኼን ሱስህን ቀንስ አልያም አቁም ብዬው ግን አላውቅም፡፡ እንዲያውም የሚያስፈልገውን ገንዘብ እሰጠው ነበር፡፡ ሳንባውና ጉበቱ ከስሎ ቢሞት ግድ አልነበረኝም፡ በእነዚህ ምሽቶች ከብዙ ታዋቂ ደራሲ እና ገጣሚ ሰዓሊ እና ምንትሶች ጋር ተዋውቂያለሁ። የብዙዎቹ መጽሐፎች አሉኝ፡፡ አብሮ ሻይ ቡና ማለቱ ከተራው ሕይወት ትንሽ ከፍ የማለት ስሜት አለው፤ አለ አይደል በቀጥታም ባይሆን “እንትናን አውቀዋለሁኮ!”… “ኧረ ባክሽ? ይኼ እንትን ፊልም የጻፈው? የእንትን መጽሐፍ ደራሲ" ...መባባል የሆነ ስሜት አለው፡፡ በተለይ ለእኔ ብዙ ነው ትርጉሙ፤ ሰው ከማያውቀው ሕመሜ ባይፈውሰኝም እንዳገግም ረድቶኛል፡፡ መልከ ጥፉ ነኝ፣ እራሴን ጠንቅቄ አውቃለሁ። መልኬ ወንዶችን አይስብም። ከእግሮቼና ከጥርሴ በስተቀር ምኔም ምኔም ዕይታ አይስብም፡፡ በእርግጥ ጓደኛዬ ማኅደረ ዓይኖችሽ ያምራሉ ትለኛለች፡፡ ሌላ ሰው ማንም ብሎኝ ስለማያውቅ እርግጠኛ አይደለሁም። ማኅደረ፣ ርግብ ነችና እባብም ቆንጆ ሆኖ የሚታያት ፍጥረት ነች፡፡ ለእሷ የሰው ልጅ በሙሉ ቆንጆ ነው፡፡ የኾነ ሆኖ አላምርምና ዕድሌ ነው ፤ ዓለም የቆንጆዎች ናት ብዬ ቁጭ ልል አልችልም፡፡ እዚሀ አስቀያሚ ሌጣ ደረቴ ውስጥ ያለው ልቤ ሥራው ደም መርጨት ብቻ አይደለምና እንደ ሰው የሚወደኝ የሚያፈቅረኝ ሰው እፈልጋለሁ። ሁልጊዜ ፍቅር እፈልጋለሁ፡፡ ዓይኖቼ ወንዶች ላይ እንደተንከራተቱ ናቸው፡፡ ግን ከ “ሃይስኩል” እስከ ኮሌጅ ፍቅረኛ ኖሮኝ አያውቅም። አደባባይ ላይ ተቁሞ ኡኡ... | የወንድ ያለኽ አይባል ነገር፡፡ ይኼ መገፋት ወደ ትምህርት ገፍቶኝ “ውይ እሷ እንደ
ወጣት አትልከሰከስ ትምህርቷ ላይ ብቻ...'' የሚባልልኝ ጎበዝ ተማሪ ሆንኩ፡፡ (ልልከስከስስ ብል...) ከዚያ በተረፈኝ ጊዜ ቤተክርስቲያን አዘወትራለሁ፡፡ ይኼም የጨዋነት ደረጃዬን ከፍ አደረገልኝ፡፡ የልቤን ናፍቆት ግን ማንም አያውቅም ነበር፡፡ እንዱ ይኼን ወረቀትሽን ወደዚያ ጣይና አግብቼ ልውሰድሽ ቢለኝ፣ ወደዚያ ወርውሬ እከተለው ነበር፡፡ በነጠላ የተሸፈነውም፣ በ'ሚንስከርት' ቡጊ ቡጊ የሚል ልቤ ነበር፡፡ ይገርመኛል ታዲያ፤ ከእህት በላይ የምታውቀኝ ጓደኛዬ ማኅደረን ጨምሮ የሚያውቁኝ ሁሉ የሚያስቡኝ ከዚህ በጣም አርቀው መሆኑ። እንዴት ዓይነት ማስመሰል ብከናነብ ነው? እላለሁ ለራሴ፡፡ ድፍን ወዳጅ ዘመዶቼ በአለፍ ገደም የሚያውቁኝ ሁሉ “ስለ ሃይሚ ጨዋነት በዐሥር ጣታችን እንፈርማለን!" ይላሉ። ከመፈረማችሁ በፊት ... በእርግጥ እንዲህ ስል ወንድ አላውቅም ማለቴ አልነበረም፡፡ አሳፋሪ ቢሆንም ወንድ ጋር መተኛት የጀመርኩት ገና የዐሥረኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ነው፡፡ ይኼንን ማንም አያውቅም ማኅደረን ጨምሮ።ምን ተብሎ ይነገራል!? የጎረቤታችን የእትዬ ሆህተ ባለቤት ጋሽ ዓለምነህ ጋር ተኛሁ ተብሎ? ለመጀመሪያ ጊዜ ወሲብ የፈጸምኩት እሱ ጋር ነበር፤ ረዥም ቀይ ነው፡፡ ለምን እንደሆነ እንጃ ሳዬው ዶክተር ነበር የሚመስለኝ፣ ኧረ ነጋዴ ነው ተብዬ ሁሉ ዶክተር ነበር የሚመስለኝ፡፡ አብረን እንድንተኛ ሲጠይቀኝ አልተግደረደርኩም(ጠዬቀኝ እንኳን አይባልም) እንዲያውም የሆነ ትልቅ ክብር ነበር የተሰማኝ። እትዬ ሆሀተ “እመብርሃንን የመሰለች" የሚባልላት ቆንጆ ሴት ነበረች፡፡ በፊልም የምናያቸውን የሀንድ ሴት ተዋናያን የመሰለች። በሙያዋ እዚህ ልደታ ፍርድ ቤት ዳኛ ነች፡፡ ሁሉም ሰው እትዬ ይላታል እንጂ፣ ያኔ ዕድሜዋ ከሰላሳ መብለጡን እንጃ፡፡ ታዲያ ባለቤቷ ጋሽ ዓለምነህን (ዓለምዬ ነዉ የምትለው) ከትምህርት ቤታችን ወረድ ብሎ የሕንፃ መሣሪያዎች መሸጫ መደብር ነበረው፣ ነጋዴ ነው፡፡ እኔና ማኅደረ ከትምህርት ቤት ወጥተን ወደ ቤታችን ስናዘግም ድንገት ከተገጣጠምን ያቺን ነጭ
ቶዮታ ኮሮላውን ያቆምና “ኑ! ግቡ'' ይለናል፡፡ እየተሸኮረመምን አንቺ ቅደሚ፣ አንቺ እየተባባልን እንገባለን፣ ይሸኜናል፡፡ ማኅደረን ሜክሲኮ ጫፍ ላይ ካወረዳት በኋላ፣ እኔ ጋር አንድ ሰፈር ስለሆንን እንቀጥላለን፡፡ ብዙ ብዙ የሚያስቅ ነገር እያወራኝ፤ ብዙ ብዙ የሚገባኝንና የማይገባኝን የሥራ ጉዳይ ምናምን እያወራኝ ...ልክ እንደ ጓደኛዉ፣ ውስጤ በጣም ነበር የሚወደው፡፡ እንደዚያም ሆኖ በኋላ መመልከቻ መስተዋቱ ደጋግሞ ዓይኑን ጣል እያደረገ ሲመለከት ብዙ ጊዜ ዓይኖቻችን ቢገጣጠሙም፤ ያው እንደሁሉም ወንድ ማኅደረን ለአጓጉል ነገር የፈለጋት ነበር የመሰለኝ፡፡ ዓይኔ ንቁ ነው። እንዲያውም ማኅደረን በኋላ “ምንድን ነው ባለትዳር አይደል እንዴ? ዐሥር ጊዜ ያፈጥብሻል"አልኳት፡፡ ደንገጥ ብላ “አፈጠጠ እንዴ?...አላዬሁትም'' አለች፡፡ ሁልጊዜ የሷን ወንዶች የማዬው እኔ ነኝ፡፡ እንዲህ ሲሆን ልለምደው ያልቻልኩት ብስጭት ውስጤ ይፈነዳል፡፡ ደንገጡር የሆንኩ ዓይነት። ማኅደረ ጋር የሚያገኙን ወንዶች ሁሉ ከመጀመሪያዋ ሰላምታ በኋላ ከነመፈጠሬ እንደረሱኝ ነው “የት ነው የምትማሩት? ...ስንተኛ ክፍል ናችሁ?...የት እየሄዳችሁ ነው? ..." የሚሉ ጥያቄዎች ሁሉ እኔን ማጀቢያ አድርገው ለማኅደረ የሚቀርቡ ነበሩ፡፡ ጥያቄያቼውን የምመልሰው እንደ አስተርጓሚ እኔ ነበርኩ፡፡ ማኅደረ ሲበዛ ዝምተኛ ናትና የእሷ አንደበት ነበርኩ፡፡ እኔ እየመለስኩ የእሷን ዓይን ለማዬት የሚታገሉት ነገር ያበሳጨኛል፤ምንም ልበል ግድ አልነበራቼውም “ራሴን ላጠፋ እየሄድኩ ነው'' ብላቼው ራሱ ግድ የሚሰጣቼው አይመስለኝም። ታዲያ አንድ ቀን ማኅደረ አባቷ ታመው፣ ከትምህርት ቤት ቀርታ ብቻዬን ታክሲ ስጠብቅ የጋሽ ዓለምነህን መኪና ከሰፈር ስትመጣ አዬኋት፡፡ ብቻዬን ስለሆንኩ እንዳላዬ ያልፈኛል ብዬ እኔም ያላዬሁት ለመምሰል እዚህና እዚያ ዓይኔን ሳቃብዝ፣ ያቺን መኪናውን ፊት ለፊቴ አቆመና መስተዋቱን ዝቅ አድርጎ “ሃይማኖት” ብሎ ጠራኝ፡፡ ታክሲ የሚጠብቀው ሰው ሁሉ ስሙ ሃይማኖት ይመስል ሁሉም ወደ እሱ
ዞረ። በእጁ ምልካት ወደ መኪናው እንድገባ ጠራኝ፣አባቴ ነበር የሚመስለው.. አላንገራገርኩም፣ የኋላውን በር ልከፍት ስታገል...ነይ እዚህ ብሎ ተንጠራርቶ የጋቢናውን በር ከፈተልኝ፡፡ ትንንሽ ነገሮች አሉ ምናልባት ለሌሎች ምንም የሆኑ፡፡ ለእኔ ግን ያች ቅጽበት የንግሥና ዙፋን ላይ የመቀመጥ ያኽል ልዩ የመከበር ስሜት ነበራት፡፡ ሁልጊዜ ይቺን የጋሽ ዓለምነህ ቶዮታ ኮሮላ መኪና ሰፈር ውስጥ በተለይ ማታ ላይ ሳያት፣ ሚስቱ እትዬ ሆህተ በክብር፣ ያኔ እኔ የተቀመጥኩበት ቦታ ላይ ተቀምጣ ነበር የማያት፡፡ ወደ ፊት የሚወደኝን ሰው አግብቼ እያልኩ የምመኜው ምኞት፣ በዚያ መስታወት አልፎ በዓይኔ የተፀነሰ ምቾት ነበር፡፡ በዚያ ላይ መኪናውን የሞላው ሽቶ...
የተላመጠ የወይራ መፋቂያ ከመሰሉ ገጣሚ ተብዬዎች ምን ጠብ ሊል?...ተጠበ ተጨንቆ ትልቅ ሥራ እንደሠራ ሰው ከመድረክ ወርደው ሲጋራቼውን በላይ በላዩ ሲያቦኑ እና መጠጣቼውን ሲገለብጡ ደሜ ይፈላል፡፡ በእርግጥ ከፍቅረኛዬ ቶማስ ይሻላሉ፤ እሱ እንዲሁ በመቆዘም ብቻ፤ ደክሞ የሚውልና የሚያድር ድብርታም ነበር። ሲጋራና መጠጡም አይቀርበት፡፡ አንድም ቀን ይኼን ሱስህን ቀንስ አልያም አቁም ብዬው ግን አላውቅም፡፡ እንዲያውም የሚያስፈልገውን ገንዘብ እሰጠው ነበር፡፡ ሳንባውና ጉበቱ ከስሎ ቢሞት ግድ አልነበረኝም፡ በእነዚህ ምሽቶች ከብዙ ታዋቂ ደራሲ እና ገጣሚ ሰዓሊ እና ምንትሶች ጋር ተዋውቂያለሁ። የብዙዎቹ መጽሐፎች አሉኝ፡፡ አብሮ ሻይ ቡና ማለቱ ከተራው ሕይወት ትንሽ ከፍ የማለት ስሜት አለው፤ አለ አይደል በቀጥታም ባይሆን “እንትናን አውቀዋለሁኮ!”… “ኧረ ባክሽ? ይኼ እንትን ፊልም የጻፈው? የእንትን መጽሐፍ ደራሲ" ...መባባል የሆነ ስሜት አለው፡፡ በተለይ ለእኔ ብዙ ነው ትርጉሙ፤ ሰው ከማያውቀው ሕመሜ ባይፈውሰኝም እንዳገግም ረድቶኛል፡፡ መልከ ጥፉ ነኝ፣ እራሴን ጠንቅቄ አውቃለሁ። መልኬ ወንዶችን አይስብም። ከእግሮቼና ከጥርሴ በስተቀር ምኔም ምኔም ዕይታ አይስብም፡፡ በእርግጥ ጓደኛዬ ማኅደረ ዓይኖችሽ ያምራሉ ትለኛለች፡፡ ሌላ ሰው ማንም ብሎኝ ስለማያውቅ እርግጠኛ አይደለሁም። ማኅደረ፣ ርግብ ነችና እባብም ቆንጆ ሆኖ የሚታያት ፍጥረት ነች፡፡ ለእሷ የሰው ልጅ በሙሉ ቆንጆ ነው፡፡ የኾነ ሆኖ አላምርምና ዕድሌ ነው ፤ ዓለም የቆንጆዎች ናት ብዬ ቁጭ ልል አልችልም፡፡ እዚሀ አስቀያሚ ሌጣ ደረቴ ውስጥ ያለው ልቤ ሥራው ደም መርጨት ብቻ አይደለምና እንደ ሰው የሚወደኝ የሚያፈቅረኝ ሰው እፈልጋለሁ። ሁልጊዜ ፍቅር እፈልጋለሁ፡፡ ዓይኖቼ ወንዶች ላይ እንደተንከራተቱ ናቸው፡፡ ግን ከ “ሃይስኩል” እስከ ኮሌጅ ፍቅረኛ ኖሮኝ አያውቅም። አደባባይ ላይ ተቁሞ ኡኡ... | የወንድ ያለኽ አይባል ነገር፡፡ ይኼ መገፋት ወደ ትምህርት ገፍቶኝ “ውይ እሷ እንደ
ወጣት አትልከሰከስ ትምህርቷ ላይ ብቻ...'' የሚባልልኝ ጎበዝ ተማሪ ሆንኩ፡፡ (ልልከስከስስ ብል...) ከዚያ በተረፈኝ ጊዜ ቤተክርስቲያን አዘወትራለሁ፡፡ ይኼም የጨዋነት ደረጃዬን ከፍ አደረገልኝ፡፡ የልቤን ናፍቆት ግን ማንም አያውቅም ነበር፡፡ እንዱ ይኼን ወረቀትሽን ወደዚያ ጣይና አግብቼ ልውሰድሽ ቢለኝ፣ ወደዚያ ወርውሬ እከተለው ነበር፡፡ በነጠላ የተሸፈነውም፣ በ'ሚንስከርት' ቡጊ ቡጊ የሚል ልቤ ነበር፡፡ ይገርመኛል ታዲያ፤ ከእህት በላይ የምታውቀኝ ጓደኛዬ ማኅደረን ጨምሮ የሚያውቁኝ ሁሉ የሚያስቡኝ ከዚህ በጣም አርቀው መሆኑ። እንዴት ዓይነት ማስመሰል ብከናነብ ነው? እላለሁ ለራሴ፡፡ ድፍን ወዳጅ ዘመዶቼ በአለፍ ገደም የሚያውቁኝ ሁሉ “ስለ ሃይሚ ጨዋነት በዐሥር ጣታችን እንፈርማለን!" ይላሉ። ከመፈረማችሁ በፊት ... በእርግጥ እንዲህ ስል ወንድ አላውቅም ማለቴ አልነበረም፡፡ አሳፋሪ ቢሆንም ወንድ ጋር መተኛት የጀመርኩት ገና የዐሥረኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ነው፡፡ ይኼንን ማንም አያውቅም ማኅደረን ጨምሮ።ምን ተብሎ ይነገራል!? የጎረቤታችን የእትዬ ሆህተ ባለቤት ጋሽ ዓለምነህ ጋር ተኛሁ ተብሎ? ለመጀመሪያ ጊዜ ወሲብ የፈጸምኩት እሱ ጋር ነበር፤ ረዥም ቀይ ነው፡፡ ለምን እንደሆነ እንጃ ሳዬው ዶክተር ነበር የሚመስለኝ፣ ኧረ ነጋዴ ነው ተብዬ ሁሉ ዶክተር ነበር የሚመስለኝ፡፡ አብረን እንድንተኛ ሲጠይቀኝ አልተግደረደርኩም(ጠዬቀኝ እንኳን አይባልም) እንዲያውም የሆነ ትልቅ ክብር ነበር የተሰማኝ። እትዬ ሆሀተ “እመብርሃንን የመሰለች" የሚባልላት ቆንጆ ሴት ነበረች፡፡ በፊልም የምናያቸውን የሀንድ ሴት ተዋናያን የመሰለች። በሙያዋ እዚህ ልደታ ፍርድ ቤት ዳኛ ነች፡፡ ሁሉም ሰው እትዬ ይላታል እንጂ፣ ያኔ ዕድሜዋ ከሰላሳ መብለጡን እንጃ፡፡ ታዲያ ባለቤቷ ጋሽ ዓለምነህን (ዓለምዬ ነዉ የምትለው) ከትምህርት ቤታችን ወረድ ብሎ የሕንፃ መሣሪያዎች መሸጫ መደብር ነበረው፣ ነጋዴ ነው፡፡ እኔና ማኅደረ ከትምህርት ቤት ወጥተን ወደ ቤታችን ስናዘግም ድንገት ከተገጣጠምን ያቺን ነጭ
ቶዮታ ኮሮላውን ያቆምና “ኑ! ግቡ'' ይለናል፡፡ እየተሸኮረመምን አንቺ ቅደሚ፣ አንቺ እየተባባልን እንገባለን፣ ይሸኜናል፡፡ ማኅደረን ሜክሲኮ ጫፍ ላይ ካወረዳት በኋላ፣ እኔ ጋር አንድ ሰፈር ስለሆንን እንቀጥላለን፡፡ ብዙ ብዙ የሚያስቅ ነገር እያወራኝ፤ ብዙ ብዙ የሚገባኝንና የማይገባኝን የሥራ ጉዳይ ምናምን እያወራኝ ...ልክ እንደ ጓደኛዉ፣ ውስጤ በጣም ነበር የሚወደው፡፡ እንደዚያም ሆኖ በኋላ መመልከቻ መስተዋቱ ደጋግሞ ዓይኑን ጣል እያደረገ ሲመለከት ብዙ ጊዜ ዓይኖቻችን ቢገጣጠሙም፤ ያው እንደሁሉም ወንድ ማኅደረን ለአጓጉል ነገር የፈለጋት ነበር የመሰለኝ፡፡ ዓይኔ ንቁ ነው። እንዲያውም ማኅደረን በኋላ “ምንድን ነው ባለትዳር አይደል እንዴ? ዐሥር ጊዜ ያፈጥብሻል"አልኳት፡፡ ደንገጥ ብላ “አፈጠጠ እንዴ?...አላዬሁትም'' አለች፡፡ ሁልጊዜ የሷን ወንዶች የማዬው እኔ ነኝ፡፡ እንዲህ ሲሆን ልለምደው ያልቻልኩት ብስጭት ውስጤ ይፈነዳል፡፡ ደንገጡር የሆንኩ ዓይነት። ማኅደረ ጋር የሚያገኙን ወንዶች ሁሉ ከመጀመሪያዋ ሰላምታ በኋላ ከነመፈጠሬ እንደረሱኝ ነው “የት ነው የምትማሩት? ...ስንተኛ ክፍል ናችሁ?...የት እየሄዳችሁ ነው? ..." የሚሉ ጥያቄዎች ሁሉ እኔን ማጀቢያ አድርገው ለማኅደረ የሚቀርቡ ነበሩ፡፡ ጥያቄያቼውን የምመልሰው እንደ አስተርጓሚ እኔ ነበርኩ፡፡ ማኅደረ ሲበዛ ዝምተኛ ናትና የእሷ አንደበት ነበርኩ፡፡ እኔ እየመለስኩ የእሷን ዓይን ለማዬት የሚታገሉት ነገር ያበሳጨኛል፤ምንም ልበል ግድ አልነበራቼውም “ራሴን ላጠፋ እየሄድኩ ነው'' ብላቼው ራሱ ግድ የሚሰጣቼው አይመስለኝም። ታዲያ አንድ ቀን ማኅደረ አባቷ ታመው፣ ከትምህርት ቤት ቀርታ ብቻዬን ታክሲ ስጠብቅ የጋሽ ዓለምነህን መኪና ከሰፈር ስትመጣ አዬኋት፡፡ ብቻዬን ስለሆንኩ እንዳላዬ ያልፈኛል ብዬ እኔም ያላዬሁት ለመምሰል እዚህና እዚያ ዓይኔን ሳቃብዝ፣ ያቺን መኪናውን ፊት ለፊቴ አቆመና መስተዋቱን ዝቅ አድርጎ “ሃይማኖት” ብሎ ጠራኝ፡፡ ታክሲ የሚጠብቀው ሰው ሁሉ ስሙ ሃይማኖት ይመስል ሁሉም ወደ እሱ
ዞረ። በእጁ ምልካት ወደ መኪናው እንድገባ ጠራኝ፣አባቴ ነበር የሚመስለው.. አላንገራገርኩም፣ የኋላውን በር ልከፍት ስታገል...ነይ እዚህ ብሎ ተንጠራርቶ የጋቢናውን በር ከፈተልኝ፡፡ ትንንሽ ነገሮች አሉ ምናልባት ለሌሎች ምንም የሆኑ፡፡ ለእኔ ግን ያች ቅጽበት የንግሥና ዙፋን ላይ የመቀመጥ ያኽል ልዩ የመከበር ስሜት ነበራት፡፡ ሁልጊዜ ይቺን የጋሽ ዓለምነህ ቶዮታ ኮሮላ መኪና ሰፈር ውስጥ በተለይ ማታ ላይ ሳያት፣ ሚስቱ እትዬ ሆህተ በክብር፣ ያኔ እኔ የተቀመጥኩበት ቦታ ላይ ተቀምጣ ነበር የማያት፡፡ ወደ ፊት የሚወደኝን ሰው አግብቼ እያልኩ የምመኜው ምኞት፣ በዚያ መስታወት አልፎ በዓይኔ የተፀነሰ ምቾት ነበር፡፡ በዚያ ላይ መኪናውን የሞላው ሽቶ...
👍37❤5
እስካሁን ያንን ቅጽበት ሳስብ ነፍሴ ሐሴት ታደርጋለች፡፡ የምድር ቆንጆ ሴቶች ሁሉ በእትዬ ሆሀተ ተወክለው የንግሥትነት ዙፋናቼውን የቀማኋቼው መስሎ ነው የሚሰማኝ። ሁልጊዜ ተሸናፊ ነኝ እንጂ፤ ነፍሴ ሽሚያና ውድድር ትወዳለች። ትንሽ እንደሄድን “ዓይናችን እያዬሽ አደግሽኮ ሃይሚ!?” አለኝ፡፡ ሃይሚ!? የምናገረው ጠፍቶኝ ዝም እንዳልኩ “ከማደግሽ፣ ቁንጅናሽ...! ስንተኛ ክፍል ሆንሽ?'' ብሎ እጁን...ያንን ንጹህ እና የሚያምር ቀኝ እጁን፣ ታፋዬ ላይ እንደ ቀልድ ጣል አደረገው፡፡ በድንገተኛው ንክኪ ስቅቅ አለኝ፣ እጁን ለመያዝ የላኩትን እጄን፣ በቀስታ ቀሚሴን ወደ ታች አስተካክዬ መለስኩት፤ግን ለመከላከል አልሞከርኩም። ዓይኖቼ ብቻ እጁ ላይ ተተከሉ፡፡ ትንሽ ዘወርወር _ አለብኝ፤ የመጀመሪያው አስተያዬት ከእጁ ጋር ተዳምሮ ስንተኛ ክፍል እንደሆንኩ ሁሉ እስኪጠፋብኝ ተደነባበርኩ፡፡ እጁ ወደ አጓጉል ቦታ ሲንቀሳቀስ ታፋና ታፋዬን በኃይል ገጥሜ፣ እጁን በእጄ ለማንሳት ያዝኩት “አይዞሽ ፈራሽ እንዴ?'' ብሎ እጁን ራሱ አነሳው፡፡ ከራሴ ክብር ይልቅ ያስቀዬምኩት ነበር የመሰለኝ “ይቅርታ ሰው ነክቶኝ ስለማያውቅ ነው'' አልኩት ፡፡ .“ግዴለም ... ያለ ነገር ነው ዕድሜሽ ነው፤ በዚያ ላይ ቆንጆ ሃሃሃሃሃ ..….እ….ስትወጭ እዚያ ፊት ለፊት ጁስ ቤቱ ጋ እጠብቅሻለሁ፣ አብረን እንሄዳለን" አለኝ፡ እንዳቀረቀርኩ “እሺ!” ብዬ ከመኪናው ወረድኩ። ዝብርቅርቅ እንዳለብኝ ትምሀርት
ቤት ውዬ ስወጣ በጉጉት ወደ ጁስ ቤቱ ተመለከትኩ መኪናዉ ቆማ ነበር።ልቤ እየደለቀች ግራና ቀኝ የሚያውቀኝ ሰው መኖር አለመኖሩን እያማተርኩ (እስኪ ምን አስፈራኝ) ወደ መኪናው ሄድኩ፡፡ በሩን ከውስጥ እየከፈተልኝ “ሃይሚ ቆንጆ ልጅ ...ግቢ ግቢ” አለኝ በፈገግታ ገብቼ ቁጭ አልኩ፡፡ ዐሥር ጊዜ አጭር የትምህርት ቤት ቀሚሴን ወደ ታች እየጎተትኩ እግሬን ለመሸፈን እሞክር ነበር፡፡ “እኔ የምልሽ ትንሽ ቆይተሺ ብትገቢ፣ ስመኝ ትጨነቅ ይሆን እንዴ?'' አለኝ፤ ስመጃ እናቴ ናት። ብዙ ጊዜ ቤተክርስቲያን ጉባኤ ካለ ከትምህርት ቤት ስወጣ በዛው ስለምሄድና አምሽቼ ስለምመለስ ምንም እንደማትል አውቃለሁ፡፡ “እዚያው ቤተስኪያኗ ሄዳ ነው" ከማለት ውጭ እናቴ ሌላ ቦታ ትሄዳለች ብላ ጠርጥራኝ አታውቅም፡፡ ግን ትንሽ መቆዬትን ምን አመጣዉ እያልኩ ምን እንደምመልስ በፍጥነት አስባለሁ ...አይሆንም ብል የሚቀረው ነገር ያጓጓኛል...ክፉኛ ጓጉቼ ነበር። እሺ ብልም ምን ይሆን የሚፈጠረው? የሚል ፍርኃት ያናውዘኛል፣ አፌ ላይ እንደመጣልኝ፣ “እኔ'ንጃ!'' አልኩ፡፡ ልምድ ያለው ሰውነውና ገብቶታል፣ ፈገግ ብሎ መኪናዋን ወደ ጦር ኃይሎች ያግለበልባት ጀመር፡፡ በዝምታ የሚያደርገውን አያለሁ። ጧት የመለሰውን እጁን እንደገና ወደ ታፋዬ ልኮ በቀስታ ቀሚሴን ወደ ላይ እንደመሰብሰብ ሲያደርገው በእጄ ያዝኩት “ሃይማኖት ..አሁን'ኮ ትልቅ፣ ቆንጆ፣ የደረሽ ልጅ ነሽ፤ አትፍሪ ...የከተማ ልጅ አይደለሽ እንዴ? በጣም ነው የወደድኩሽ” አለኝ፡፡ እጄን አላላሁ፤ እጁ ታፋዬ ላይ በቀስታ እየተንቀሳቀሰ የባጥ የቆጡን ያወራኛል፡፡ ምኑንም አልሰማውም፤ ወደ አንድ መኖሪያ ቤት ወደሚመስል ግቢ ገብቶ፣ መኪናውን አቆመና እንውረድ አለኝ፡፡
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
ቤት ውዬ ስወጣ በጉጉት ወደ ጁስ ቤቱ ተመለከትኩ መኪናዉ ቆማ ነበር።ልቤ እየደለቀች ግራና ቀኝ የሚያውቀኝ ሰው መኖር አለመኖሩን እያማተርኩ (እስኪ ምን አስፈራኝ) ወደ መኪናው ሄድኩ፡፡ በሩን ከውስጥ እየከፈተልኝ “ሃይሚ ቆንጆ ልጅ ...ግቢ ግቢ” አለኝ በፈገግታ ገብቼ ቁጭ አልኩ፡፡ ዐሥር ጊዜ አጭር የትምህርት ቤት ቀሚሴን ወደ ታች እየጎተትኩ እግሬን ለመሸፈን እሞክር ነበር፡፡ “እኔ የምልሽ ትንሽ ቆይተሺ ብትገቢ፣ ስመኝ ትጨነቅ ይሆን እንዴ?'' አለኝ፤ ስመጃ እናቴ ናት። ብዙ ጊዜ ቤተክርስቲያን ጉባኤ ካለ ከትምህርት ቤት ስወጣ በዛው ስለምሄድና አምሽቼ ስለምመለስ ምንም እንደማትል አውቃለሁ፡፡ “እዚያው ቤተስኪያኗ ሄዳ ነው" ከማለት ውጭ እናቴ ሌላ ቦታ ትሄዳለች ብላ ጠርጥራኝ አታውቅም፡፡ ግን ትንሽ መቆዬትን ምን አመጣዉ እያልኩ ምን እንደምመልስ በፍጥነት አስባለሁ ...አይሆንም ብል የሚቀረው ነገር ያጓጓኛል...ክፉኛ ጓጉቼ ነበር። እሺ ብልም ምን ይሆን የሚፈጠረው? የሚል ፍርኃት ያናውዘኛል፣ አፌ ላይ እንደመጣልኝ፣ “እኔ'ንጃ!'' አልኩ፡፡ ልምድ ያለው ሰውነውና ገብቶታል፣ ፈገግ ብሎ መኪናዋን ወደ ጦር ኃይሎች ያግለበልባት ጀመር፡፡ በዝምታ የሚያደርገውን አያለሁ። ጧት የመለሰውን እጁን እንደገና ወደ ታፋዬ ልኮ በቀስታ ቀሚሴን ወደ ላይ እንደመሰብሰብ ሲያደርገው በእጄ ያዝኩት “ሃይማኖት ..አሁን'ኮ ትልቅ፣ ቆንጆ፣ የደረሽ ልጅ ነሽ፤ አትፍሪ ...የከተማ ልጅ አይደለሽ እንዴ? በጣም ነው የወደድኩሽ” አለኝ፡፡ እጄን አላላሁ፤ እጁ ታፋዬ ላይ በቀስታ እየተንቀሳቀሰ የባጥ የቆጡን ያወራኛል፡፡ ምኑንም አልሰማውም፤ ወደ አንድ መኖሪያ ቤት ወደሚመስል ግቢ ገብቶ፣ መኪናውን አቆመና እንውረድ አለኝ፡፡
ይቀጥላል...
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
👍45
ሰው የሚማረው፣
አንድም ከፊደል፣
አንድም ከመከራ ነው፤
አንድ ቃል ከፊደል ጥበብ፣
አንድ ቃል ከመከራ መዝገብ፣
አንድም በሳር "ሀ" ብሎ፣
አንድም በአሣር "ዋ" ብሎ፤
🎴ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
አንድም ከፊደል፣
አንድም ከመከራ ነው፤
አንድ ቃል ከፊደል ጥበብ፣
አንድ ቃል ከመከራ መዝገብ፣
አንድም በሳር "ሀ" ብሎ፣
አንድም በአሣር "ዋ" ብሎ፤
🎴ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍21❤4
#የማይቻል_አንድ ነገር
እዉነት - ቤት ስትሰራ
ዉሸት - ላግዝ ካለች፣
ምስማር ካቀበለች፣
"ቤቱም አልተሰራ
እዉነትም አልኖረች።
🎴ጌትነት እንየው🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
እዉነት - ቤት ስትሰራ
ዉሸት - ላግዝ ካለች፣
ምስማር ካቀበለች፣
"ቤቱም አልተሰራ
እዉነትም አልኖረች።
🎴ጌትነት እንየው🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍14👏4
እባክሽ አትሂጂ…..
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-14
///
ሰው ለጥቅሙ ሲል ነው የወደደኝ ብለህ አትማረር፡፡ እኛም እኮ ፀሀይን የምንወዳትና የምናፈቅራት ለሙቀቷ እና ለብርሀኗ ስንል ነው፤ለጥቅማችን ብለን..ከለበለዚያ እሰከመፈጠሯም ትዝ ላትለን ትችል ነበር፡፡ለጥቅም ሲባል መጥላትና መጉደት እንጂ ለጥቅም ሲሉ ማፍቀር ምን ክፍታ አለው፡፡
በሶስተኛው ቀን እራሴ በጥዋት እቤት ድረስ ሄድኩና በራሴ መኪና ልዕልትን ከነህመምተኛ ባለቤቷ ጭኜ ወደጓደኛዬ ኪኒሊክ ሄድን…ከጓደኛዬ ጋር ቀድሜ ተነጋግሬና ሁሉ ነገር አመቻችቼ ስለነበር ቀጥታ እንደደረስን ያለምንም ውጣ ውረድ በህመምተኛ ተሸክርካሪ አልጋ ላይ ተኝቶ በነርሶች እየተገፋ ማሽኑ ወደሚገኝበት ክፍል ሲወሰድ እኔና ልዕልት በረንዳ ላይ በሚገኝ ወንበር ላይ ጎን ለጎን ተቀምጠን መጠበቅ ጀመርን፡፡ይሄ ምርመራ ምንም ነገር እንደማይፈይድለትና ..እስከአሁን ስለመስፍን በሽታ ከምናውቀው ዝርዝር መረጃ ተጨማሪ እንደማያሳውቀን በእርግጠኝነት አውቃለሁ፡፡.ግን ይሄንን ምርመራ እንዲያደርግ የፈለኩት ከወንድሟ አቤል ጋር የተነጋርነውን ነገር ለማድረግ ሀሳቡን ለልዕልት ለማቅረብ እንዲያግዘኝና መነሻ ሰበበ ምክንት እንዲሆነኝ ብቻ ስለፈለኩ ነው፡፡በአንድ ሰዓት ሁሉ ነገር ተጠናቀቀና ..ውጤቱን በማግስቱ መጥተን እንድንወስድ ተነገሮን በሽተኛውን ተረከብን፡፡ጭኜ እንዳመጣኋቸው መልሼ ጭኜ ወደቤት ወሰደኳቸውና ጎን ለጎን ተሸክመን መልሰን መደበኛ አልጋው ላይ አስተኛነው..ጎን ለጎን ሆነን ከመኪናው አውርደን ስንሸከመው አንደኛው እጄና እጇን አንድ ላይ አቆላልፈን በሌለኛው እጃችን ትከሻውን ደግፈን ስለነበረ..ልቤን የሚያቀልጥ ጥልቅ ሙቀት ነበር የለቀቀችብኝ…የእሷን እጅ የጨበጠው እጄ ለዘላለም ባለበት ሆኖ ቢቀጥል ምኞቴ ነበር….የተሸከምነው ባለቤቷ እንኳን የህፃን ልጅ ያህል ስላልከበደኝ ምን አለw መኪናውም ቀርቶ ከሆስፒታል ጀምሮ እንደዚህ እጅ ለእጅ እንዳቆላለፍን ተሸክመነው በመጣን ኖር የሚል የጅል ምኞት በውስጤ በመብቀሉ ሳልፈልግ ፈገግ ለማለት ተገድጄ ነበር፡፡
‹‹በይ ልሄድ…ነገ ውጤቱን ተቀብዬ አመጣለሁ፡፡ ››
‹‹እንዴ ዶክተር..የምሳ ሰዓት ደርሷል ..ቁጭ በልና ምሳ በልተህ ትሄዳለህ›› ተላማጠቺኝ፡፡
‹‹አይ ቸኩላለሁ…በፍጥነት ወደሆስፒታል መመለስ አለብኝ..እዛው ቀለል ያለ ነገር እበላለሁ፡፡››
‹‹በጣም አስቸገርኩህ አይደል….ቆያ ጠብቀኝ ብሩን ይዤልህ ልምጣ››
ደነገጥኩ …‹‹የምኑን ብር?››
‹‹ለህክምና የከፈልከውን ነዋ…እርግጥ መጠኑን ስላላወቅኩ አሁን በርሳዬ ውስጥ ያለው ሀያ ሺ ብር ብቻ ነው….የጎደለውን ነገ አሞላላሁ፡፡››
‹‹የሄድንበት ኪኒኒክ የጓደኛዬ ነው ብዬሽ ነበር…. አዲስ ማሽን ስላስገባ እንደማስመረቂያ በነፃ ነው የሰራልኝ፡፡››
‹በፍፅም ዶ/ር..እንዲህ አይት ነገር ልቀበል አልችልም…ጠብቀኝ..››ተንደርድራ ወደ መኝታ ቤቷ ገባች፡፡ተንደርሬ ሳሎኑን ለቅቄ ወጣሁ፡፡ የውጩን በራፍ ከፈትኩና መኪናዬን ውስጥ ገብቼ ተፈተለኩ… ልትደርስብኝ ስትንደረደር አላቆምኩላትም፡፡ከሰፈር ራቅ እንዳልኩ ያቺ ዘወትር ለልዕልት መስጠት ያቃተኝን አበባ ሀምሳ ብር እየተቀበለች የምትቀበለኝ እብድ ቦታዋ ላይ ቁጭ ብላ መሬቱን ስትቆረቆር አገኘኋትና እንደወትሮዬ የአስፓቱን ጠርዝ ይዤ…..በዝግታ እየነዳው ስሮ ስደርስ አቆምኩ፡፡
‹‹እሼ እንዴት ነሽ?››
ቀና ብላ እንኳን ሳታየኝ‹‹50 ብር ካልከፈልከኝ..አበባውን አልቀበልህም፡፡ ››አለችኝ፡፡
ፈገግ አልኩ፡፡ኪሴ ገባሁና 50 ብር በማውጣት ሰጠኋት›ቀና አለችና በቆሻሻ የጠቋቆረ እጇን ዘረጋጀችና 50 ብሩን እየተቀበለቺኝ‹‹ ጎበዝ.. አሁን ደግሞ አበባውን አምጣ..››
‹‹ዛሬ አበባው የለም››
ክው ብላ ደነገጠች…በመደንገጧ እኔም አብሬያት ደነገጥኩ‹‹ምነው ..እሺ ብላ ተቀበለችህ እንዴ?››
‹‹አይ ዛሬ እረስቼው ….ባዶ እጄን ነወ የሄድኩት››
‹‹ወንዶች ድሮውንም ስልቹዎች ናቸሁ…ቶሎ ተስፋ ትቆርጣላችሁ….እሼ ዛሬ አበባውን ለመቀበል ዝግጁ የሆነችበት ቀን ቢሆንስ? ከሰርክ ማለት አይደል…?ለማንኛውም እንካ ››ብላ 50 ብሩን ወደእኔ ዘረጋች፡፡
‹‹ምን ላድርገው..ሰጠውሽ እኮ…ያንቺው ነው››
‹‹አይ..እኔ በነፃ ብር መቀበል አልወድም….በተለይ ከወንዶች የብላሽ ብር መቀበል መዘዙ ብዙ ነው››
ይህቺ ልጅ እብድ ነች ፋላስፋ አልኩና እጃን እንዳንከረፈፈች መኪናውን አስፈንጥሬ ጉዞዬን ቀጠልኩ….፡፡
በማግስቱ ደወልኩና ትናንት የተገናኘንበት ቦታ ቀጠርኳት..እያለከለከች መጣች።
ከሰላምታ በኃላ ቀጥታ ወደ ጥያቄ ነው የገባችም።
‹‹ዶ/ር ውጤቱ እንዴት ነው...?የተለየ ነገር አለው?››
‹‹ብዙም አይደል ...ብቻ?››
‹‹ብቻ ምን?››
‹‹ጓደኛዬ ማለት ምርመራውን ያደረግንበት ኪሊኒክ ባለቤት ከእኔ የተለየ እምነት ነው ያለው?››
‹‹ማለት ?››
‹‹እሱ ውጭ ሄዶ ቢታከም ቢያንስ የመዳን እድሉን አሁን ካለበት በ10 ፐርሰንት ይጨምራል የሚል ነው።››
‹‹አሪፍ ነዎ...አንተስ ዶ/ር ?በእሱ አስተያየት ላይ ሀሳብህ እንዴት ነው?››በመንሰፍሰፍ ጠየቀችኝ፡፡
‹‹እሱ እንዳለው ትንሽም ቢሆን የመዳን ቻንሱን በጥቂት ፐርሰንትም ቢሆን ሊጨምር ይችል ይሆናል ..ግን አቅሙ ይኖርሻል ወይ?ከዛ በኃላስ ካልተሳካስ?እሱ ነው የሚያሳስበኝ፡፡››
በአጠቃላይ ወሸት መጥፎና አሳፋሪ ነገር ነው፡፡መሀላ በገቡለት በሞያ ሽፋን መዋሸት ግን የስብእና መቆሸሽን ያሳያል፡፡እራሴን ጠላሁት፡፡ምን እየሰራሁ ነው?
እሷ ቀጠለች"እንዴ ዶ/ር አንድ ፐርሰንት ተጨማሪ እድል የሚያስገኝለት ከሆነ ከመሞከር ወደኃላ አልልም...አቅሙ ላልከው የግድ ነው እንደምንም እሞክራለሁ?ካልሆነ ቤቴን አስይዤ ከባንክ እበደራለሁ ወይም ሙሉ በሙሉ ሸጠውና አነስ ያለ ማረፊያ ገዝቼ በተቀረው አሳክመዎለሁ..."
‹‹ቁርጠኝነቷን ሳይ ፋዝዝ ብዬ በትኩረት አጤናት ጀመር››
‹‹ይሄውልሽ ልዕልት ..ቀስ ብለሽ ተረጋግተሽ ከዘመድም ከወዳጅም ጋር ምከሪበት...ከዛ መልሰን እናወራበትና ››
‹‹አይ ወስኜለሁ..በዚህ ጉዳይ ከማንም ጋር መደራደር አልፈልግም…የሚያግዘኝ ከላ ከጎኔ ይሰለፍ…አሻረኝ የሚል ሰው ደግሞ ከመንገዴ ገለል ይበል ››ብላ ተሰናብታኝ ወደ ቤቷ ተመለሰች፡፡የሆነውን ለወንድሞ ደውዬ ነገርኩት፡፡በደስታ ፈነጠዘና ረጅም ምስጋና አዥጎደጎደልኝ፡፡
///
ፍቅር ማለት …ሁለት ልቦች በአንድ ቅኝት አንድ አይነት የልብ-ምት ሲያሰሙ ማለት ነው….፡፡፡ግን እኔና ልእልት እኮ በአንድ አይነት ቅኝት አንድ አይነት የልብ ምት እያስደመጥን አይደለም፡፡የእኔ ልብ ለእሷ ሲንዷዷ…የእሷ ልብ ደግሞ ለመስፍን ይንዷቆዶቃል፡፡የእሱስ ልብ ለማን ይሆን የሚመታው..አሁንም ለብዙ ሴቶች በአንድ ጊዜ ይመታ ይሆን ወይስ ፍቅር የሚባለውን ነገር አለም ረስቶ በህይወት ስለመቆየት ብቻ እያሰበ ይሆን…?
ሚስቶቻችንን እንዳፈቀርናቸው እስከመጨረሻ መዝለቅ አንችልም..ጥቂት አመት አብረን ከኖርን እናቶቻቸን ይሆናሉ።አብዛኛዎቹ የተሳካላቸው ሚስቶች ባለቤቷን እንደመጀመሪያ ልጇ ነው የምታየው... የምትንከባከበውም።ልክ አሁን ልዕልተ መስፍን ለተባለው ባሏ እንደምታደርገው ማለት ነው፡፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-14
///
ሰው ለጥቅሙ ሲል ነው የወደደኝ ብለህ አትማረር፡፡ እኛም እኮ ፀሀይን የምንወዳትና የምናፈቅራት ለሙቀቷ እና ለብርሀኗ ስንል ነው፤ለጥቅማችን ብለን..ከለበለዚያ እሰከመፈጠሯም ትዝ ላትለን ትችል ነበር፡፡ለጥቅም ሲባል መጥላትና መጉደት እንጂ ለጥቅም ሲሉ ማፍቀር ምን ክፍታ አለው፡፡
በሶስተኛው ቀን እራሴ በጥዋት እቤት ድረስ ሄድኩና በራሴ መኪና ልዕልትን ከነህመምተኛ ባለቤቷ ጭኜ ወደጓደኛዬ ኪኒሊክ ሄድን…ከጓደኛዬ ጋር ቀድሜ ተነጋግሬና ሁሉ ነገር አመቻችቼ ስለነበር ቀጥታ እንደደረስን ያለምንም ውጣ ውረድ በህመምተኛ ተሸክርካሪ አልጋ ላይ ተኝቶ በነርሶች እየተገፋ ማሽኑ ወደሚገኝበት ክፍል ሲወሰድ እኔና ልዕልት በረንዳ ላይ በሚገኝ ወንበር ላይ ጎን ለጎን ተቀምጠን መጠበቅ ጀመርን፡፡ይሄ ምርመራ ምንም ነገር እንደማይፈይድለትና ..እስከአሁን ስለመስፍን በሽታ ከምናውቀው ዝርዝር መረጃ ተጨማሪ እንደማያሳውቀን በእርግጠኝነት አውቃለሁ፡፡.ግን ይሄንን ምርመራ እንዲያደርግ የፈለኩት ከወንድሟ አቤል ጋር የተነጋርነውን ነገር ለማድረግ ሀሳቡን ለልዕልት ለማቅረብ እንዲያግዘኝና መነሻ ሰበበ ምክንት እንዲሆነኝ ብቻ ስለፈለኩ ነው፡፡በአንድ ሰዓት ሁሉ ነገር ተጠናቀቀና ..ውጤቱን በማግስቱ መጥተን እንድንወስድ ተነገሮን በሽተኛውን ተረከብን፡፡ጭኜ እንዳመጣኋቸው መልሼ ጭኜ ወደቤት ወሰደኳቸውና ጎን ለጎን ተሸክመን መልሰን መደበኛ አልጋው ላይ አስተኛነው..ጎን ለጎን ሆነን ከመኪናው አውርደን ስንሸከመው አንደኛው እጄና እጇን አንድ ላይ አቆላልፈን በሌለኛው እጃችን ትከሻውን ደግፈን ስለነበረ..ልቤን የሚያቀልጥ ጥልቅ ሙቀት ነበር የለቀቀችብኝ…የእሷን እጅ የጨበጠው እጄ ለዘላለም ባለበት ሆኖ ቢቀጥል ምኞቴ ነበር….የተሸከምነው ባለቤቷ እንኳን የህፃን ልጅ ያህል ስላልከበደኝ ምን አለw መኪናውም ቀርቶ ከሆስፒታል ጀምሮ እንደዚህ እጅ ለእጅ እንዳቆላለፍን ተሸክመነው በመጣን ኖር የሚል የጅል ምኞት በውስጤ በመብቀሉ ሳልፈልግ ፈገግ ለማለት ተገድጄ ነበር፡፡
‹‹በይ ልሄድ…ነገ ውጤቱን ተቀብዬ አመጣለሁ፡፡ ››
‹‹እንዴ ዶክተር..የምሳ ሰዓት ደርሷል ..ቁጭ በልና ምሳ በልተህ ትሄዳለህ›› ተላማጠቺኝ፡፡
‹‹አይ ቸኩላለሁ…በፍጥነት ወደሆስፒታል መመለስ አለብኝ..እዛው ቀለል ያለ ነገር እበላለሁ፡፡››
‹‹በጣም አስቸገርኩህ አይደል….ቆያ ጠብቀኝ ብሩን ይዤልህ ልምጣ››
ደነገጥኩ …‹‹የምኑን ብር?››
‹‹ለህክምና የከፈልከውን ነዋ…እርግጥ መጠኑን ስላላወቅኩ አሁን በርሳዬ ውስጥ ያለው ሀያ ሺ ብር ብቻ ነው….የጎደለውን ነገ አሞላላሁ፡፡››
‹‹የሄድንበት ኪኒኒክ የጓደኛዬ ነው ብዬሽ ነበር…. አዲስ ማሽን ስላስገባ እንደማስመረቂያ በነፃ ነው የሰራልኝ፡፡››
‹በፍፅም ዶ/ር..እንዲህ አይት ነገር ልቀበል አልችልም…ጠብቀኝ..››ተንደርድራ ወደ መኝታ ቤቷ ገባች፡፡ተንደርሬ ሳሎኑን ለቅቄ ወጣሁ፡፡ የውጩን በራፍ ከፈትኩና መኪናዬን ውስጥ ገብቼ ተፈተለኩ… ልትደርስብኝ ስትንደረደር አላቆምኩላትም፡፡ከሰፈር ራቅ እንዳልኩ ያቺ ዘወትር ለልዕልት መስጠት ያቃተኝን አበባ ሀምሳ ብር እየተቀበለች የምትቀበለኝ እብድ ቦታዋ ላይ ቁጭ ብላ መሬቱን ስትቆረቆር አገኘኋትና እንደወትሮዬ የአስፓቱን ጠርዝ ይዤ…..በዝግታ እየነዳው ስሮ ስደርስ አቆምኩ፡፡
‹‹እሼ እንዴት ነሽ?››
ቀና ብላ እንኳን ሳታየኝ‹‹50 ብር ካልከፈልከኝ..አበባውን አልቀበልህም፡፡ ››አለችኝ፡፡
ፈገግ አልኩ፡፡ኪሴ ገባሁና 50 ብር በማውጣት ሰጠኋት›ቀና አለችና በቆሻሻ የጠቋቆረ እጇን ዘረጋጀችና 50 ብሩን እየተቀበለቺኝ‹‹ ጎበዝ.. አሁን ደግሞ አበባውን አምጣ..››
‹‹ዛሬ አበባው የለም››
ክው ብላ ደነገጠች…በመደንገጧ እኔም አብሬያት ደነገጥኩ‹‹ምነው ..እሺ ብላ ተቀበለችህ እንዴ?››
‹‹አይ ዛሬ እረስቼው ….ባዶ እጄን ነወ የሄድኩት››
‹‹ወንዶች ድሮውንም ስልቹዎች ናቸሁ…ቶሎ ተስፋ ትቆርጣላችሁ….እሼ ዛሬ አበባውን ለመቀበል ዝግጁ የሆነችበት ቀን ቢሆንስ? ከሰርክ ማለት አይደል…?ለማንኛውም እንካ ››ብላ 50 ብሩን ወደእኔ ዘረጋች፡፡
‹‹ምን ላድርገው..ሰጠውሽ እኮ…ያንቺው ነው››
‹‹አይ..እኔ በነፃ ብር መቀበል አልወድም….በተለይ ከወንዶች የብላሽ ብር መቀበል መዘዙ ብዙ ነው››
ይህቺ ልጅ እብድ ነች ፋላስፋ አልኩና እጃን እንዳንከረፈፈች መኪናውን አስፈንጥሬ ጉዞዬን ቀጠልኩ….፡፡
በማግስቱ ደወልኩና ትናንት የተገናኘንበት ቦታ ቀጠርኳት..እያለከለከች መጣች።
ከሰላምታ በኃላ ቀጥታ ወደ ጥያቄ ነው የገባችም።
‹‹ዶ/ር ውጤቱ እንዴት ነው...?የተለየ ነገር አለው?››
‹‹ብዙም አይደል ...ብቻ?››
‹‹ብቻ ምን?››
‹‹ጓደኛዬ ማለት ምርመራውን ያደረግንበት ኪሊኒክ ባለቤት ከእኔ የተለየ እምነት ነው ያለው?››
‹‹ማለት ?››
‹‹እሱ ውጭ ሄዶ ቢታከም ቢያንስ የመዳን እድሉን አሁን ካለበት በ10 ፐርሰንት ይጨምራል የሚል ነው።››
‹‹አሪፍ ነዎ...አንተስ ዶ/ር ?በእሱ አስተያየት ላይ ሀሳብህ እንዴት ነው?››በመንሰፍሰፍ ጠየቀችኝ፡፡
‹‹እሱ እንዳለው ትንሽም ቢሆን የመዳን ቻንሱን በጥቂት ፐርሰንትም ቢሆን ሊጨምር ይችል ይሆናል ..ግን አቅሙ ይኖርሻል ወይ?ከዛ በኃላስ ካልተሳካስ?እሱ ነው የሚያሳስበኝ፡፡››
በአጠቃላይ ወሸት መጥፎና አሳፋሪ ነገር ነው፡፡መሀላ በገቡለት በሞያ ሽፋን መዋሸት ግን የስብእና መቆሸሽን ያሳያል፡፡እራሴን ጠላሁት፡፡ምን እየሰራሁ ነው?
እሷ ቀጠለች"እንዴ ዶ/ር አንድ ፐርሰንት ተጨማሪ እድል የሚያስገኝለት ከሆነ ከመሞከር ወደኃላ አልልም...አቅሙ ላልከው የግድ ነው እንደምንም እሞክራለሁ?ካልሆነ ቤቴን አስይዤ ከባንክ እበደራለሁ ወይም ሙሉ በሙሉ ሸጠውና አነስ ያለ ማረፊያ ገዝቼ በተቀረው አሳክመዎለሁ..."
‹‹ቁርጠኝነቷን ሳይ ፋዝዝ ብዬ በትኩረት አጤናት ጀመር››
‹‹ይሄውልሽ ልዕልት ..ቀስ ብለሽ ተረጋግተሽ ከዘመድም ከወዳጅም ጋር ምከሪበት...ከዛ መልሰን እናወራበትና ››
‹‹አይ ወስኜለሁ..በዚህ ጉዳይ ከማንም ጋር መደራደር አልፈልግም…የሚያግዘኝ ከላ ከጎኔ ይሰለፍ…አሻረኝ የሚል ሰው ደግሞ ከመንገዴ ገለል ይበል ››ብላ ተሰናብታኝ ወደ ቤቷ ተመለሰች፡፡የሆነውን ለወንድሞ ደውዬ ነገርኩት፡፡በደስታ ፈነጠዘና ረጅም ምስጋና አዥጎደጎደልኝ፡፡
///
ፍቅር ማለት …ሁለት ልቦች በአንድ ቅኝት አንድ አይነት የልብ-ምት ሲያሰሙ ማለት ነው….፡፡፡ግን እኔና ልእልት እኮ በአንድ አይነት ቅኝት አንድ አይነት የልብ ምት እያስደመጥን አይደለም፡፡የእኔ ልብ ለእሷ ሲንዷዷ…የእሷ ልብ ደግሞ ለመስፍን ይንዷቆዶቃል፡፡የእሱስ ልብ ለማን ይሆን የሚመታው..አሁንም ለብዙ ሴቶች በአንድ ጊዜ ይመታ ይሆን ወይስ ፍቅር የሚባለውን ነገር አለም ረስቶ በህይወት ስለመቆየት ብቻ እያሰበ ይሆን…?
ሚስቶቻችንን እንዳፈቀርናቸው እስከመጨረሻ መዝለቅ አንችልም..ጥቂት አመት አብረን ከኖርን እናቶቻቸን ይሆናሉ።አብዛኛዎቹ የተሳካላቸው ሚስቶች ባለቤቷን እንደመጀመሪያ ልጇ ነው የምታየው... የምትንከባከበውም።ልክ አሁን ልዕልተ መስፍን ለተባለው ባሏ እንደምታደርገው ማለት ነው፡፡
👍48❤7
ምንም ምርጫ አልሰጠችኝም...እድሜ ለወንድሟ ቅርቃር ውስጥ ገብቼያለሁ።አሁን በቃ መሄድ የለበትም እዚሁ እናክመዋለን ብላትም አሻፈረኝ አለች።እሺ ሌላ ሰው ወይም ወንድሙ ይዛት ይሂድ ብትባልም እኔ እያለሁ እንዴት ተደርጎ?አለች። አይኔ እያየ ለእሬሳ የቀረበ ሰው ለማዳን የልጆቾን ማሳደጊያ የወደፊት ጥሪቷን ሰብስባ ለማጥፋት ከመወሰኗም በላይ ልጆቾን ለቤተሠቦቾ ትታ እኔን አውላላ ሜዳ ላይ ጥላኝ በበአድ ሀገር… በአድ የሆነ ፈተና ለመጋፈጥ ልትሄድ ነው?‹‹መጀመሪያ እንግዲያው ለመሄድ በቁርጠኝነት ከወሰንሽ እኔም ልከተልሽ›› ልላት አስቤ ነው።ቆይቼ በመረጋጋት ሳሰላስለው የሚሆን ሆኖ አላገኘሁትም...‹‹ስራዬን እንዴት አደርጋለሁ?ሰውን በተለይ እናቴን ምን ብዬ አሳምናታለሁ...?እሺ እንደምንም ቀባጥሬና ለፍልፌ እናቴን ማሳመን ብችል እንኳን እራሷን ልዕልትን ምን ብዬ ነው ባልሽን ለማስታመም ስራዬን እርግፍ አድርጌ ትቼ አንቺን ተከትዬ ልሂድ ልላት የምችለው?እራስን ሙሉ በሙሉ አጋልጦ ትዝብት ላይ ከመውደቅ በስተቀር እሷን አሳምኖ ይሁንታ ማስገኘት የሚችል ሀሳብ አይደለም...በዚህ የተነሳ አራት ቀን ሌት ያለማቋረጥ ጨጓራዬ እስኪቆስል ድረስ ካሰብኩ በኃላ አንድ አደገኛና አስጠሊታ ውሳኔ ወሰንኩ...አሁን ውሳኔዬን ተግባራዊ ለማድረግ ሙሉ ዝግጅቴን አጠናቅቄ ወደ እነ ልዕልት ቤት እየሄድኩ ነው።
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
ይቀጥላል...
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
👍32❤4
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ፅዮን እና ታዲዬስ እሁድ ከምሽቱ 12 ሰዓት ሀዋሳ ሴንትራል ሆቴል ቁጭ ብላው እሷ ለስላሳ እሱ ቢራ አዛው እየተጐነጩ ያዘዙትን መክሰስ በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡የምረቃ በዓሉ ካለፈ በኃላ በሣምንታቸው ዛሬ መገናኘታቸው ነው፡፡‹‹እሺ ፅዮን ለምን ግን ወይን ነገር አትሞክሪም ነበር?››
<<አንደኛ አልኮል የሚባል ነገር ሞክሬ አላውቅም ...ሁለተኛ የማያየው ዓይኔ ሳያንስ ጠጥቼ እምሮዬንም እንዳያይ አድርጌ እንዴት ልሆን ነው?››
‹‹አይ ሳታበዢ ማለቴ እኮ ነው፡፡››
‹‹ያው መጠጣት ከጀመርኩ ቢያንስ አንድ ብርጭቆ መጨረሴ ይቀራል..ያ ማለት ደግሞ እኔን ለማስከር በቂ መጠን ነው…ግድ የለህም ለስላሳው ይብቃኝ፡፡››
‹‹ያው ብትሰክሪም እኮ እኔ አብሬሽ አለሁ ብዬ ነው፡፡››
‹‹አይ እኔ በራሴ ድክመት እራሴን ጥዬ ሰውን ደግፉኝ ማለት አይመቸኝም፡፡››
‹‹ተቀብያለሁ››አለ በጠንካራ መንፈሷ ተደስቶባት፡፡
‹‹ፂ ስለበቀደሙ ጉዳይ እንድናወራ ነው ዛሬ የቀጠርኩሽ››ወደዋናው ቁምነገር ድንገት ገባ።
‹‹ይመቸኛል..እኔም እንደዛ እንደሆነ ተስፋ በማድረግ ነው የመጣሁት..ቀጥል፡፡››
‹‹እንዴት እንደምቀጥል አላውቅም፤ብቻ…..››
‹‹ታዲ ..እኔ የ28 ዓመት ወጣት ነኝ፤በህይወቴ ብዙ ውጣ ውረድ ያየው ሰው ነኝ.. ህይወት ነጩንም ሆነ ጥቁሩን ክፍሎቿን በማፈራረቅ አሳይታኛለች፡፡አንድን ነገር ፈልጌዋለሁና የግድ አገኘዋለሁ ማለት እንዳልሆነ አውቃለሁ፡፡››
‹‹በህይወትማ ምንም ነገር ከልብሽ አገኘዋለሁ ብለሽ ካሰብሽ ታገኚዋለሽ፡፡››
‹‹አውቃለሁ....የሆነ ነገር አገኛለሁ ብለህ ከልብህ ከተመኘህ፤ ምኞትህንም ለማሳካት በሙሉ ጉልበትህ ከተንቀሳቀስክ የማይሳካልህ ነገር እንደሌለ እኔም አምናለሁ፤ይሄ ግን ፍቅር ላይ ሲሆን ከሚሰራበት ጊዜ ይልቅ የማይሰራበት ጊዜ ይበልጣል፡፡››
‹‹እንዴት እንዲህ ልትይ ቻልሽ…?ከፍቅር አምላክ ጋር ትንሽ የተቀያየማችሁ ይመስላል፡፡››
‹‹ትንሽ አልከው...ምን ትንሽ ብቻ ...ለአምስት አመት ተኮራርፈን በደረሰበት ላልደርስ ተማምለን… ሳይደርስብኝ ሳልደርስበት ጥሩ ጊዜ አሳልፈን ነበር ፡፡››
‹‹ታዲያ እንዴት ሆናችሁ?››
‹‹ምን እንዴት ሆናችሁ አለው... አንተን ሳገኝ መሀላዬን አፍርሼ ደጅ እየፀናሁ እያየኸኝ?››
‹‹ደጅ ጽናት አልሽው፤ለማንኛውም እስኪ በምን ተኮራርፋችሁ እንደነበረ ብትነግሪኝ ? ማለት ደስ ካለሽ…..››
ዝም አለች... ጭንቅላቷ ወደታች ተደፋ‹‹…ምን መሰለህ......››ብላ ልትቀጥል ስትል ያዘዙት መክሰስ መጣና ቀረበላቸው፡እየተጎራረሱ በሉ..ከጨረሡ በኃላ አብረው ወደ እጅ መታጠቢያው በመሄድ ታጠቡና ወደመቀመጫቸው ተመለሱ፡፡ታዲዬስ ሁለተኛ ቢራውን አዘዘ..ዛሬ ካለወትሮው ጠጣ ጠጣ አሰኝቶታል፡፡
‹‹ምነው ዝም አልከኝ ...?››አለችው ልትጀምርለት የነበረውን ታሪኳን እንድትቀጥልለት ባለመጠየቁ ቅር ብሏት...
‹‹ኧረ ዝም አላልኩሽም ….ዝም ስላልሽ እኮ ዝምታሽን ላለመረበሽ ብዬ ነው፤እኔ ዝምታዬን ከሚረቡሹኝ ንግግሬን ቢያቋርጡኝ ይሻለኛል፡፡››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው….ግን አሁን ዝምታ ውስጥ ስላልሆንኩ አትረብሸኝም
...ይሄውልህ ታዲ እኔ የሻሸመኔ ልጅ ነኝ፡፡ ትውልዴ እስከተወሰነ ጊዜም እድገቴም እዛ ነው፡፡ አባቴን እና እናቴን አላውቃቸውም ማለቴ በአካል አላውቃቸውም...ያሳደገችኝ የአባቴ እናት አያቴ ነች ... እናቴ ገና አንድ አመት ሳይሞላኝ ነው አባቴ ክንድ ላይ ጥላኝ ሀገሩን ጥላ የጠፋችው፡፡ ከአንድ አመት በኃላ አባቴም በተራው ሁኔታዎች ስልችት ሲሉት እኔን ለእናቱ ሰጥቶኝ ውትድርና ተቀጥሮ ለጦርነት ወደ ሰሜን ይሄዳል፡፡
ከዛ በኃላ አያቴ ያለቻትን አንድ ክፍል ቤት በደባልነት አንድ ደደፎ ለሚባል ከገጠር ለትምህርት ለመጣ ልጅ አከራይታ ከእሱ ከምታገኘው ገቢ በተጨማሪም በደካማ አቅሟ ጠላ እየጠመቀች አንዳንዴም አረቄ እያወጣች በመሸጥ እኔን ማሳደግ ትጀምራለች ፡፡ስምንት ዓመት ሲሞላኝ ግን ያልታሰበ ችግር ተፈጠረ..
ዓይኖቼን ይጋርደኝ ጀመር ..በወቅቱ አያቴ እንኳን ለህክምና ለሆዴም መሙያ የሚሆን ሳንቲም ለማግኘት በመከራ ነበር ሚሳካላት…፡፡
ባቅሟ የቻለችውን ፀበሉንም የባህል መድሀኒቱንም ብትሞክርልኝም ከቀን ወደቀን እየባሰብኝ መጥቶ ከአንድ አመት በኃላ ሙሉ በሙሉ ሁለቱም አይኖቼ ታወሩ..ከዛ ትምህርቴንም ከሁለተኛ ክፍል ግማሽ ላይ አቆረጥኩ፡፡አያቴ ግራ ገባት ፡፡በሚመጣው አመት ግን ያ እቤታችን በደባልነት ይኖር የነበር ያልኩህ ተማሪው ልጅ ሚሽኖቹ ጋር ተሯሩጦ በአዳሪነት አስገባኝ፡፡ ይገርምሀል አያቴን ልክ እንደእናቱ ነበር የሚወዳት... እሷም ከእኔ ለይታ አታየውም ነበር እንዲሁ ስሙ ተከራይ ተባለ እንጂ እኛ የምንበላውን ይበላል እሱ የሚበላውን እንበላለን ስናጣ አብረን እንራባለን፡
እኔ ሚሽን በአዳሪነት ከገባሁ በኃላ አያቴ ጋር እኖር ከነበረው ኑሮ በተሻለ ሁኔታ እኖር ጀመር፤ ትምህርቴንም በጥሩ ሁኔታ መከታተል ጀመርኩ፤ድንገት ግን ምን እንደተፈጠረ ታውቃለህ? ብቸኛ ዘመዴ የሆነችው አያቴ ሞተች፡፡በወቅቱ የ5ተኛ ክፍል ተማሪ ነበርኩ… ዕድሜዬም ወደ 14 አካባቢ ተጠግቶ ነበር ..በጣም ነው የከበደኝ፡፡ ለመጽናናት በጣም አስቸግሬ ነበር፡፡ይገርምሀል እቤታችንን ተከራይቶ ነበር ያልኩህ ልጅ በወቅቱ አስረኛ ክፍል ደርሶ ነበር፡፡በአያቴን ሞት በጣም ነበር ያዘነው…፡፡
ከዛ እኔን መንከባከብ የእሱ ኃላፊነት እንደሆነ ነበር የሚያስበው፤ በሳምንት ሁለት ቀን እየመጣ ይጠይቀኝ ነበር፤ደግሞ ሲመጣ ባዶ እጁን አይመጣም..ደብተር፣እስኪሪብቶ፣የፀጉር ቅባት፣ማበጠሪያ፣ፓንት ...ብቻ የማይገዛልኝ ነገር አልነበረም፤ካጣ ካጣ የ 25 ሳንቲም ማስቲካም ቢሆን ይዞልኝ ይመጣል..ደግሞ እኮ የሚገርመው እሱም ምንም የሌለው የደሀ ገበሬ ልጅ መሆኑ ነው፡፡ ግማሽ ቀን ይማራል ኑሮውን ለመደጎም ደግሞ ግማሽ ቀን ጋራዥ ይሰራል...ከዛ በሚያገኛት ሽርፍራፊ ገንዘብ ነበር ለእኔ የሚያስፈልገኝን ነገር ይገዛልኝ የነበርው፡፡
በዛ ላይ የቤት ኪራዬን በየወሩ ቀን እንኳን ሳያስተጎጉል አምጥቶ ይሰጠኛል…ተወው ይቅር አያስፈልገኝም ብለውም አይሰማኝም...‹ነገ ብትቸገሪ ለአንድ ነገር ይሆንሻል.. አስቀምጪው >> ይለኛል...እኔ ደግሞ የተለየ ወጪ ስለሌለኝ እጄ ላይ እየተጠራቀመ ሲበዛብኝ አንድ የምወዳት አስተማሪዬ ጋር ማስቀመጥ ጀመርኩ፡፡
እንዲህ እንዲህ እያለ ቀናቶች እየነጐዱ እኔም እያደግኩ በትምህርቴም እየገፋሁ መጣሁ..በነገራችን ላይ ሙዚቃ መሳሪያ መነካካት የጀመርኩት እዛው ሻሸመኔ አይነስውራን ትምህርት ቤት እያለሁ ነበር፡፡
ስምንተኛ ክፍል ስደርስ ደደፎ 12ተኛ ክፍል ጨርሶ ነጥብ ስላልመጣለት መንጃ ፍቃድ አውጥቶ ሹፌር ሆነ፡፡በዚህን ጊዜ በሳምንት ሁለት ቀን መምጣቱን አቁሞ በሳምንት አንዴ
..አንዳንዴም በአስራአምስት ቀን አንዴ ይመጣ
ጀመር፡፡ሲመጣ ታዲያ ይዞልኝ የሚመጣውን
ነገር አትጠይቀኝ ... ምንም የሚቀረው ነገር
አልነበረም፤ለእኔ አይደለም ለጓደኞቼ እራሱ ይተርፍ ነበር፡፡ የጽዮን ወንድም መጣ ከተባለ ጓደኞቼ በሙሉ ጥርስ በጥርስ ነበር
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ፅዮን እና ታዲዬስ እሁድ ከምሽቱ 12 ሰዓት ሀዋሳ ሴንትራል ሆቴል ቁጭ ብላው እሷ ለስላሳ እሱ ቢራ አዛው እየተጐነጩ ያዘዙትን መክሰስ በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡የምረቃ በዓሉ ካለፈ በኃላ በሣምንታቸው ዛሬ መገናኘታቸው ነው፡፡‹‹እሺ ፅዮን ለምን ግን ወይን ነገር አትሞክሪም ነበር?››
<<አንደኛ አልኮል የሚባል ነገር ሞክሬ አላውቅም ...ሁለተኛ የማያየው ዓይኔ ሳያንስ ጠጥቼ እምሮዬንም እንዳያይ አድርጌ እንዴት ልሆን ነው?››
‹‹አይ ሳታበዢ ማለቴ እኮ ነው፡፡››
‹‹ያው መጠጣት ከጀመርኩ ቢያንስ አንድ ብርጭቆ መጨረሴ ይቀራል..ያ ማለት ደግሞ እኔን ለማስከር በቂ መጠን ነው…ግድ የለህም ለስላሳው ይብቃኝ፡፡››
‹‹ያው ብትሰክሪም እኮ እኔ አብሬሽ አለሁ ብዬ ነው፡፡››
‹‹አይ እኔ በራሴ ድክመት እራሴን ጥዬ ሰውን ደግፉኝ ማለት አይመቸኝም፡፡››
‹‹ተቀብያለሁ››አለ በጠንካራ መንፈሷ ተደስቶባት፡፡
‹‹ፂ ስለበቀደሙ ጉዳይ እንድናወራ ነው ዛሬ የቀጠርኩሽ››ወደዋናው ቁምነገር ድንገት ገባ።
‹‹ይመቸኛል..እኔም እንደዛ እንደሆነ ተስፋ በማድረግ ነው የመጣሁት..ቀጥል፡፡››
‹‹እንዴት እንደምቀጥል አላውቅም፤ብቻ…..››
‹‹ታዲ ..እኔ የ28 ዓመት ወጣት ነኝ፤በህይወቴ ብዙ ውጣ ውረድ ያየው ሰው ነኝ.. ህይወት ነጩንም ሆነ ጥቁሩን ክፍሎቿን በማፈራረቅ አሳይታኛለች፡፡አንድን ነገር ፈልጌዋለሁና የግድ አገኘዋለሁ ማለት እንዳልሆነ አውቃለሁ፡፡››
‹‹በህይወትማ ምንም ነገር ከልብሽ አገኘዋለሁ ብለሽ ካሰብሽ ታገኚዋለሽ፡፡››
‹‹አውቃለሁ....የሆነ ነገር አገኛለሁ ብለህ ከልብህ ከተመኘህ፤ ምኞትህንም ለማሳካት በሙሉ ጉልበትህ ከተንቀሳቀስክ የማይሳካልህ ነገር እንደሌለ እኔም አምናለሁ፤ይሄ ግን ፍቅር ላይ ሲሆን ከሚሰራበት ጊዜ ይልቅ የማይሰራበት ጊዜ ይበልጣል፡፡››
‹‹እንዴት እንዲህ ልትይ ቻልሽ…?ከፍቅር አምላክ ጋር ትንሽ የተቀያየማችሁ ይመስላል፡፡››
‹‹ትንሽ አልከው...ምን ትንሽ ብቻ ...ለአምስት አመት ተኮራርፈን በደረሰበት ላልደርስ ተማምለን… ሳይደርስብኝ ሳልደርስበት ጥሩ ጊዜ አሳልፈን ነበር ፡፡››
‹‹ታዲያ እንዴት ሆናችሁ?››
‹‹ምን እንዴት ሆናችሁ አለው... አንተን ሳገኝ መሀላዬን አፍርሼ ደጅ እየፀናሁ እያየኸኝ?››
‹‹ደጅ ጽናት አልሽው፤ለማንኛውም እስኪ በምን ተኮራርፋችሁ እንደነበረ ብትነግሪኝ ? ማለት ደስ ካለሽ…..››
ዝም አለች... ጭንቅላቷ ወደታች ተደፋ‹‹…ምን መሰለህ......››ብላ ልትቀጥል ስትል ያዘዙት መክሰስ መጣና ቀረበላቸው፡እየተጎራረሱ በሉ..ከጨረሡ በኃላ አብረው ወደ እጅ መታጠቢያው በመሄድ ታጠቡና ወደመቀመጫቸው ተመለሱ፡፡ታዲዬስ ሁለተኛ ቢራውን አዘዘ..ዛሬ ካለወትሮው ጠጣ ጠጣ አሰኝቶታል፡፡
‹‹ምነው ዝም አልከኝ ...?››አለችው ልትጀምርለት የነበረውን ታሪኳን እንድትቀጥልለት ባለመጠየቁ ቅር ብሏት...
‹‹ኧረ ዝም አላልኩሽም ….ዝም ስላልሽ እኮ ዝምታሽን ላለመረበሽ ብዬ ነው፤እኔ ዝምታዬን ከሚረቡሹኝ ንግግሬን ቢያቋርጡኝ ይሻለኛል፡፡››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው….ግን አሁን ዝምታ ውስጥ ስላልሆንኩ አትረብሸኝም
...ይሄውልህ ታዲ እኔ የሻሸመኔ ልጅ ነኝ፡፡ ትውልዴ እስከተወሰነ ጊዜም እድገቴም እዛ ነው፡፡ አባቴን እና እናቴን አላውቃቸውም ማለቴ በአካል አላውቃቸውም...ያሳደገችኝ የአባቴ እናት አያቴ ነች ... እናቴ ገና አንድ አመት ሳይሞላኝ ነው አባቴ ክንድ ላይ ጥላኝ ሀገሩን ጥላ የጠፋችው፡፡ ከአንድ አመት በኃላ አባቴም በተራው ሁኔታዎች ስልችት ሲሉት እኔን ለእናቱ ሰጥቶኝ ውትድርና ተቀጥሮ ለጦርነት ወደ ሰሜን ይሄዳል፡፡
ከዛ በኃላ አያቴ ያለቻትን አንድ ክፍል ቤት በደባልነት አንድ ደደፎ ለሚባል ከገጠር ለትምህርት ለመጣ ልጅ አከራይታ ከእሱ ከምታገኘው ገቢ በተጨማሪም በደካማ አቅሟ ጠላ እየጠመቀች አንዳንዴም አረቄ እያወጣች በመሸጥ እኔን ማሳደግ ትጀምራለች ፡፡ስምንት ዓመት ሲሞላኝ ግን ያልታሰበ ችግር ተፈጠረ..
ዓይኖቼን ይጋርደኝ ጀመር ..በወቅቱ አያቴ እንኳን ለህክምና ለሆዴም መሙያ የሚሆን ሳንቲም ለማግኘት በመከራ ነበር ሚሳካላት…፡፡
ባቅሟ የቻለችውን ፀበሉንም የባህል መድሀኒቱንም ብትሞክርልኝም ከቀን ወደቀን እየባሰብኝ መጥቶ ከአንድ አመት በኃላ ሙሉ በሙሉ ሁለቱም አይኖቼ ታወሩ..ከዛ ትምህርቴንም ከሁለተኛ ክፍል ግማሽ ላይ አቆረጥኩ፡፡አያቴ ግራ ገባት ፡፡በሚመጣው አመት ግን ያ እቤታችን በደባልነት ይኖር የነበር ያልኩህ ተማሪው ልጅ ሚሽኖቹ ጋር ተሯሩጦ በአዳሪነት አስገባኝ፡፡ ይገርምሀል አያቴን ልክ እንደእናቱ ነበር የሚወዳት... እሷም ከእኔ ለይታ አታየውም ነበር እንዲሁ ስሙ ተከራይ ተባለ እንጂ እኛ የምንበላውን ይበላል እሱ የሚበላውን እንበላለን ስናጣ አብረን እንራባለን፡
እኔ ሚሽን በአዳሪነት ከገባሁ በኃላ አያቴ ጋር እኖር ከነበረው ኑሮ በተሻለ ሁኔታ እኖር ጀመር፤ ትምህርቴንም በጥሩ ሁኔታ መከታተል ጀመርኩ፤ድንገት ግን ምን እንደተፈጠረ ታውቃለህ? ብቸኛ ዘመዴ የሆነችው አያቴ ሞተች፡፡በወቅቱ የ5ተኛ ክፍል ተማሪ ነበርኩ… ዕድሜዬም ወደ 14 አካባቢ ተጠግቶ ነበር ..በጣም ነው የከበደኝ፡፡ ለመጽናናት በጣም አስቸግሬ ነበር፡፡ይገርምሀል እቤታችንን ተከራይቶ ነበር ያልኩህ ልጅ በወቅቱ አስረኛ ክፍል ደርሶ ነበር፡፡በአያቴን ሞት በጣም ነበር ያዘነው…፡፡
ከዛ እኔን መንከባከብ የእሱ ኃላፊነት እንደሆነ ነበር የሚያስበው፤ በሳምንት ሁለት ቀን እየመጣ ይጠይቀኝ ነበር፤ደግሞ ሲመጣ ባዶ እጁን አይመጣም..ደብተር፣እስኪሪብቶ፣የፀጉር ቅባት፣ማበጠሪያ፣ፓንት ...ብቻ የማይገዛልኝ ነገር አልነበረም፤ካጣ ካጣ የ 25 ሳንቲም ማስቲካም ቢሆን ይዞልኝ ይመጣል..ደግሞ እኮ የሚገርመው እሱም ምንም የሌለው የደሀ ገበሬ ልጅ መሆኑ ነው፡፡ ግማሽ ቀን ይማራል ኑሮውን ለመደጎም ደግሞ ግማሽ ቀን ጋራዥ ይሰራል...ከዛ በሚያገኛት ሽርፍራፊ ገንዘብ ነበር ለእኔ የሚያስፈልገኝን ነገር ይገዛልኝ የነበርው፡፡
በዛ ላይ የቤት ኪራዬን በየወሩ ቀን እንኳን ሳያስተጎጉል አምጥቶ ይሰጠኛል…ተወው ይቅር አያስፈልገኝም ብለውም አይሰማኝም...‹ነገ ብትቸገሪ ለአንድ ነገር ይሆንሻል.. አስቀምጪው >> ይለኛል...እኔ ደግሞ የተለየ ወጪ ስለሌለኝ እጄ ላይ እየተጠራቀመ ሲበዛብኝ አንድ የምወዳት አስተማሪዬ ጋር ማስቀመጥ ጀመርኩ፡፡
እንዲህ እንዲህ እያለ ቀናቶች እየነጐዱ እኔም እያደግኩ በትምህርቴም እየገፋሁ መጣሁ..በነገራችን ላይ ሙዚቃ መሳሪያ መነካካት የጀመርኩት እዛው ሻሸመኔ አይነስውራን ትምህርት ቤት እያለሁ ነበር፡፡
ስምንተኛ ክፍል ስደርስ ደደፎ 12ተኛ ክፍል ጨርሶ ነጥብ ስላልመጣለት መንጃ ፍቃድ አውጥቶ ሹፌር ሆነ፡፡በዚህን ጊዜ በሳምንት ሁለት ቀን መምጣቱን አቁሞ በሳምንት አንዴ
..አንዳንዴም በአስራአምስት ቀን አንዴ ይመጣ
ጀመር፡፡ሲመጣ ታዲያ ይዞልኝ የሚመጣውን
ነገር አትጠይቀኝ ... ምንም የሚቀረው ነገር
አልነበረም፤ለእኔ አይደለም ለጓደኞቼ እራሱ ይተርፍ ነበር፡፡ የጽዮን ወንድም መጣ ከተባለ ጓደኞቼ በሙሉ ጥርስ በጥርስ ነበር
👍73❤8
የሚሆኑት...ታዲያ በዛን ወቅት እሱ ሄዶ መልሶ
እስኪመጣ ድረስ ክፉኛ በናፍቆት እሰቃይ
ጀመር፡፡ ሳይደበዝዝ በውስጤ ተቀርጾ የቀረው
የእሱ ምስል ብቻ ነበር..ከነሙሉ ቁመናው ፤
አቋሙ ፤ መልኩ የማውቀው አንድ ሰው ቢኖር እሱ ብቻ ነበር፡፡ አሁን አሁን ሳስበው
ይገርመኛል...እኔም ልክ ዕዳ እንዳለበት አድርጌ ነበር የማስበው፡፡ከሳምንት አሳልፎ የመጣ ጊዜ
አኮርፈዋለሁ፣እነጫነጭበታለሁ፣የማለቅስበት ጊዜ ሁሉ አለ..ታዲያ ለምኖኝ
ተለማምጦኝ፤በስጦታ ደልሎኝ ይታረቀኛል፡፡
ከዛ ልክ 10ረኛ ክፍል እንደጨረስኩ እሱ የሚሰራበት መስሪያ ቤት ሙሉ በሙሉ ወደአዲስ አበባ ቀየረው፡፡እዛ ከገባ ደግሞ በወር አንድ ቀን እንኳን መጥቶ ሊጠይቀኝ ይከብደዋል፡፡ጭንቅ ሆነ ፤ሲያማክረኝ አበድኩበት..ሌላ ስራ እዛው ሻሸመኔ ለማግኘት ቢጥርም በፍጥነት ሊሳካለት አልቻለም፡፡ከዛ አብሬህ እሄዳለው አልኩት... ይገርምሀል የተደሰተው መደሰት ልነግርህ አልችልም፡፡ለካ በፊቱንም እሱ እሺ አትለኝም ብሎ ፈርቶ እንጄ ፍላጎቱ እንደዛ ነበር፡፡
ከዛ ተያይዘን ወደ አዲስ አበባ ሄድን፡፡ እንደእድል ሆኖ ደግሞ የሚሰራበት መስሪያ ቤት ሁለት ክፍል መኖሪያ ቤት ከነሙሉ ዕቃው ሰጥቶት ስለነበርን ያለችግር ኑሮን ጀመርን፡፡ የ11ኛ ክፍልም ትምህርቴንም እዛው ቀጠልኩ... ኮንትራት ታክሲ ይዞልኝ ከቤት እየተመላለስኩ ማለት ነው፡፡››
ንግግሯን አቋረጠችና እጇን ሚሪንዳ ወደ ያዘው ብርጭቆ ሰዳ በማንሳት አንዴ ገርገጭ አድርጋ ጉሮሮዋን አራሰችና‹‹ታዲ››ብላ ጠራችው
‹‹አቤት..፡፡››
<<ወሬዬ አልሰለቸህም አይደል...ይቅርታ ይሄን ታሪክ ከጀመርኩ ለማሳጠር ስለሚከብደኝ ነው...፡፡››
‹‹ኧረ ቀጥይ በጣም ተመስጬ ነው እያዳመጥኩሽ ያለሁት... ከፈለግሽ እስከነገም ቢሆን አዳምጥሻለሁ፡፡›› አላትና አንድ ሌላ ቢራ እንድትጨምርለት ለአስተናጋጇ በምልክት ነግሯት ትኩረቱን ወደ ጽዮን መለሰ፡፡
ቀጠለች‹‹....ከዛ በየቀኑ አብሬው እየኖርኩ... አብሬው እያደርኩ ...ትምህርቴን እየተማርኩ አስደሳች ህይወት መኖር ጀመርኩ፡፡ ይገርምሀል እድሜዬ 18 ወይም 19 አካባቢ ደርሶ ትልቅ ልጃገረድ ሆኜ እያለሁ እንኳን እሱ ምኔ እንደሆነ ?በምንስ ሂሳብ አብሬው እንደምኖር ? ለአንድም ቀን አስቤበት እና ተጨንቄበት አላውቅም ነበር፡፡ለምንስ እጨነቃለሁ... ለእኔ እሱ ማለት መላ ነገሬ ነው፤እናት አባቴ አክስት አጐቴ ነው…እሱ ስላለኝ ነው ስለምንም ጉዳይ የማልጨነቀው..
አባቴ ውትድርና ብሎ እንደወጣ ይሙት
አይሙት ሳይታወቅ በዛው ቢቀርም አልፎ አልፎ ባጋጣሚ ከማስታወስ ውጭ እሱን እያሰብኩ በሀዘን ተክዤ አላውቅም፤ ስለእናቴም አንዳንዴ እንኳን
እንደው ባገኘዋት ብዬ ማስበው ያኔ እንደው
በዛ ጮርቃ እድሜዬ ጡት እንኳን በደንብ ጠብቼ ሳልጠግብ ለአባቴ ጥላኝ እብስ ያለችው ምን አጋጥሞት ይሆን . ?.አባቴስ ምን
ያህል ቢበድላት ነው…?በጣም ቢመራት
እንኳን እንዴት ይዛኝ ለመሄድ ሳትሞክር
....?.እነዚህን የመሳሰሉትን የዕድሜ ልክ ጥያቄዎቼን እንድትመልስልኝ ብዬ እንጂ
እናትነቷ አጓጉቶኝ ..
እንክብካቤዋ ናፍቆኝ
አልነበረም፡፡
ደደፎ ሁሉን ነገር ነበር የሚሰጠኝ፤ምንም ያጣሁት ምንም የጎደለብኝ ነገር አልነበረም ፡፡ እንዳልኩት ሆኖ ነው፤ የጠየቅኩትን ሰጥቶኝ ፤የፈለግኩትን ገዝቶልኝ ነው፡፡ሲጠራኝ እንኳን በስሜ አይደለም.. ኪያ ነበር የሚለኝ ..<ኪያ
>ማለት የኦሮሚኛ ቃል ሲሆን ወደ አማርኛ ሲመለስ‹ የእኔ፤ የግሌ›› ማለት ነው ትምህርቴን ስጨርስ በፍላጎቴ ያሬድ ገብቼ ፒያኖ እንዳጠና አመቻቸልኝ፡፡ጀመርኩ፤ሁለት ዓመት ከተማርኩ በኃላ ችግር ተፈጠረ፡፡ትዝ ይለኛል እሁድ ቀን ነው 8 ሰዓት አካባቢ.......
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
እስኪመጣ ድረስ ክፉኛ በናፍቆት እሰቃይ
ጀመር፡፡ ሳይደበዝዝ በውስጤ ተቀርጾ የቀረው
የእሱ ምስል ብቻ ነበር..ከነሙሉ ቁመናው ፤
አቋሙ ፤ መልኩ የማውቀው አንድ ሰው ቢኖር እሱ ብቻ ነበር፡፡ አሁን አሁን ሳስበው
ይገርመኛል...እኔም ልክ ዕዳ እንዳለበት አድርጌ ነበር የማስበው፡፡ከሳምንት አሳልፎ የመጣ ጊዜ
አኮርፈዋለሁ፣እነጫነጭበታለሁ፣የማለቅስበት ጊዜ ሁሉ አለ..ታዲያ ለምኖኝ
ተለማምጦኝ፤በስጦታ ደልሎኝ ይታረቀኛል፡፡
ከዛ ልክ 10ረኛ ክፍል እንደጨረስኩ እሱ የሚሰራበት መስሪያ ቤት ሙሉ በሙሉ ወደአዲስ አበባ ቀየረው፡፡እዛ ከገባ ደግሞ በወር አንድ ቀን እንኳን መጥቶ ሊጠይቀኝ ይከብደዋል፡፡ጭንቅ ሆነ ፤ሲያማክረኝ አበድኩበት..ሌላ ስራ እዛው ሻሸመኔ ለማግኘት ቢጥርም በፍጥነት ሊሳካለት አልቻለም፡፡ከዛ አብሬህ እሄዳለው አልኩት... ይገርምሀል የተደሰተው መደሰት ልነግርህ አልችልም፡፡ለካ በፊቱንም እሱ እሺ አትለኝም ብሎ ፈርቶ እንጄ ፍላጎቱ እንደዛ ነበር፡፡
ከዛ ተያይዘን ወደ አዲስ አበባ ሄድን፡፡ እንደእድል ሆኖ ደግሞ የሚሰራበት መስሪያ ቤት ሁለት ክፍል መኖሪያ ቤት ከነሙሉ ዕቃው ሰጥቶት ስለነበርን ያለችግር ኑሮን ጀመርን፡፡ የ11ኛ ክፍልም ትምህርቴንም እዛው ቀጠልኩ... ኮንትራት ታክሲ ይዞልኝ ከቤት እየተመላለስኩ ማለት ነው፡፡››
ንግግሯን አቋረጠችና እጇን ሚሪንዳ ወደ ያዘው ብርጭቆ ሰዳ በማንሳት አንዴ ገርገጭ አድርጋ ጉሮሮዋን አራሰችና‹‹ታዲ››ብላ ጠራችው
‹‹አቤት..፡፡››
<<ወሬዬ አልሰለቸህም አይደል...ይቅርታ ይሄን ታሪክ ከጀመርኩ ለማሳጠር ስለሚከብደኝ ነው...፡፡››
‹‹ኧረ ቀጥይ በጣም ተመስጬ ነው እያዳመጥኩሽ ያለሁት... ከፈለግሽ እስከነገም ቢሆን አዳምጥሻለሁ፡፡›› አላትና አንድ ሌላ ቢራ እንድትጨምርለት ለአስተናጋጇ በምልክት ነግሯት ትኩረቱን ወደ ጽዮን መለሰ፡፡
ቀጠለች‹‹....ከዛ በየቀኑ አብሬው እየኖርኩ... አብሬው እያደርኩ ...ትምህርቴን እየተማርኩ አስደሳች ህይወት መኖር ጀመርኩ፡፡ ይገርምሀል እድሜዬ 18 ወይም 19 አካባቢ ደርሶ ትልቅ ልጃገረድ ሆኜ እያለሁ እንኳን እሱ ምኔ እንደሆነ ?በምንስ ሂሳብ አብሬው እንደምኖር ? ለአንድም ቀን አስቤበት እና ተጨንቄበት አላውቅም ነበር፡፡ለምንስ እጨነቃለሁ... ለእኔ እሱ ማለት መላ ነገሬ ነው፤እናት አባቴ አክስት አጐቴ ነው…እሱ ስላለኝ ነው ስለምንም ጉዳይ የማልጨነቀው..
አባቴ ውትድርና ብሎ እንደወጣ ይሙት
አይሙት ሳይታወቅ በዛው ቢቀርም አልፎ አልፎ ባጋጣሚ ከማስታወስ ውጭ እሱን እያሰብኩ በሀዘን ተክዤ አላውቅም፤ ስለእናቴም አንዳንዴ እንኳን
እንደው ባገኘዋት ብዬ ማስበው ያኔ እንደው
በዛ ጮርቃ እድሜዬ ጡት እንኳን በደንብ ጠብቼ ሳልጠግብ ለአባቴ ጥላኝ እብስ ያለችው ምን አጋጥሞት ይሆን . ?.አባቴስ ምን
ያህል ቢበድላት ነው…?በጣም ቢመራት
እንኳን እንዴት ይዛኝ ለመሄድ ሳትሞክር
....?.እነዚህን የመሳሰሉትን የዕድሜ ልክ ጥያቄዎቼን እንድትመልስልኝ ብዬ እንጂ
እናትነቷ አጓጉቶኝ ..
እንክብካቤዋ ናፍቆኝ
አልነበረም፡፡
ደደፎ ሁሉን ነገር ነበር የሚሰጠኝ፤ምንም ያጣሁት ምንም የጎደለብኝ ነገር አልነበረም ፡፡ እንዳልኩት ሆኖ ነው፤ የጠየቅኩትን ሰጥቶኝ ፤የፈለግኩትን ገዝቶልኝ ነው፡፡ሲጠራኝ እንኳን በስሜ አይደለም.. ኪያ ነበር የሚለኝ ..<ኪያ
>ማለት የኦሮሚኛ ቃል ሲሆን ወደ አማርኛ ሲመለስ‹ የእኔ፤ የግሌ›› ማለት ነው ትምህርቴን ስጨርስ በፍላጎቴ ያሬድ ገብቼ ፒያኖ እንዳጠና አመቻቸልኝ፡፡ጀመርኩ፤ሁለት ዓመት ከተማርኩ በኃላ ችግር ተፈጠረ፡፡ትዝ ይለኛል እሁድ ቀን ነው 8 ሰዓት አካባቢ.......
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍69❤13😁3
#ሸሌ_ነኝ
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
"ነይ እዚህ ጋር ! ልብስሽን አውልቀሽ ውስጥ ሳትገቢ...ብርድ ልብሱ ላይ ተኚ" ሲለኝ፣ ልማድ ሆኖብኝ መግደርደር ዳድቶኝ ነበር።
ድሮ፤ ልጃገረድ እንዳለሁ ግዜ መሽኮርመም። ሰው እንጂ ሴት ያልሆኑኩ መስሎኝ፣ ሥጋ ሸጬ እንጀራ ልገዛ ያልመጣሁ መስሎኝ።
አንገቴን እንደሰበርኩ ወደ አልጋው ሄድኩ ሲያገኘኝ እሄድ እንደነበረው አይደለም አካሄዴ።ሰበር ሰካ የለውም፣ ዕዩኝ ዕዩኝ የለውም፣ ተገዝቶ ወደ ሚታረድበት ቦታ እንደሚሄድ በግ ነው አካሄዴ።
ገዥዬ የማያውቀኝ፣ ሰው ፊት ልብሴን ሳወልቅ የመጀመርያዬ እንጀሆነ አያውቅም።
ገዥዬ፣ በገንዘብ ተገዝቼ ከወንድ ለመተኛት ስመጣ የመጀመርያዬ እንደሆነ አያውቅም።
ገዥዬ፣ ለዚህ ስራ ድንግል እንደሆንኩ አያውቅም።
ልብሴን ማውለቅ ሳልጀምር እየፈራው፣ "ይቅርታ....መብራቱን ታጠፋው?" አልኩት።
ዞር ብሎ ዐየኝና፣ "ሃሃ...ሃ! ታሾፌያለሽ እንዴ.? ለምንድን ነው የማጠፋው...? አለኝ። ይስቃል።
ፈራሁ ብለው አያምንም። በሰቀቀን ዝም ብዬ ማውለቅ ጀመርኩ። የአልጋው ጫፍ ላይ ኩምትር እንዳልኩ ድንገት እስካሁን መኖሩን ያላወኩት ብርድ አንዘፈዘፈኝ። ሳል ጀመረኝ።
ይሄን ግዜ ሰውየው ዞር ብሎ ዐየኝና ፤ "ምነው.. ብርድ.. ቲቢ.. ምናምን አለብሽ እንዴ?" አለኝ።
"አይ...በርዶኝ ነው...አያመኝም...አሁን በርዶኝ ነው..." ብዬ ብርድ ልብስ ውስጥ ገባሁ።
"ኖኖ!...ከላይ ሁኚ...አትግቢ..." አለኝ ቶሎ ብሎ ፣ ቀጭን ትዛዝ ነበር።
እምቢ ብዬ መሄድ እንደማልችል ማወቁ አስከፋኝ። እሺ ብዬው ስለመጣሁ እምቢ ብዬ ስለማልሄድ እርግጠኛ መሆኑን ሳውቅ ከፋኝ። ከነሳሌ ከብርድ ልብስ ወጣሁ። መጥቶ አጠገቤ ተኛ። ሰውነቴ በፍርሃት ተንዘፈዘፈ። ነውስጥ ሱሪ ብቻ ሲቀረው ዕርቃኑን ነው።
እግዜር በሚያውቀው፣ ከማላውቀው ሰው ቤት ለማደር መምጣት አልፈለግኩም ነበር።
የማላውቀው ሰው እጁቹን ጭኖቼ መሀል አስገብቶ እንዲፈነጭ አልፈለግኩም ነበር።
የማላውቀው ሰው ጆሮዬን ተጠግቶ እንዲያቃትትብኝ አልፈለግኩም ነበር። ግን ሰውየው አስገድዶ አላመጣኝም። አልደፈረኝም።
ያስገደደኝ ኑሮ ነው።
የደፈረኝ ድህነት ነው።
ሲነጋና ከኔ ጋር ያለውን ጣጣውን ሲጨርስ፣ የሰጠኝን አምስት መቶ አዳዳስ ብሮች እንደያዝኩ በትእዛዝ ያወለኩትን ልብሴን በከፍተኛ ፍጥነት ለበስኩ። ያወለኩት ክብሬ ግን አልጋው ላይ ቀርቷል።
"ቅዳሜ እመጣለሁ....ማን ብዬ ላስጠራሽ ?" አለኝ በተኛበት።
እንድሄድ ፈልጓል። አገልግሎቴ አብቅቷል። አሁን እንደተፋቀ የሞባይል ካርድ ነኝ። አሁን እንደተጫረ የክብሪት ዕንጨት ነኝ። በድጋሚ በጉጉት የሚያየኝ በሚቀጥለው ቅዳሜ መጥቼ እፎይ ማለት ሲያምረው ነው። ስሜን ነግሬው ዞር አልኩና ቦርሳዬን አንጠልጥዬ ለመሄድ ስዞር፣
"ማነሽ...እ...በሩን በደንብ ዝጊው!" አለኝ፣ አልጋው ላይ ተገላብጦ ጀርባውን እየሰጠኝ። ፊት እንኳን የማይገባኝ ሰው መሆኔን ሲነግረኝ ነው በጀርባው የሚያናግረኝ፣ የሚታወስ ሰም እንደሌለኝ ሲነግረኝ ነው ማነሽ ያለኝ።
ይሄን ሳስብ ተዛባሁ፣ ተዛነፍኩ።
ካለ አጥንት እንደተፈጠረ ሰው ሰውነቴ ለመቆምም ለመሄድም እምቢ እያለ ወደ ታክሲ ተራው ሄድኩ። ተኝቶ የነጋለት ሰው ይተራመሳል።
ታክሲው ውስጥ ገብቼ መስኮቱን ደገፍ አልኩና ያለ እቅድ ስቅስቅ ብዬ ማልቀስ ጀመርኩ። ከዐይኔ ግድብ የሚፈሰው እንባ ጉንጬቼ ላይ የሚያደርቅ ሳይሆን አዋሽ ወንዝ ለመግባት ያልም ይመስል ይንዠቀዠቃል።
ከክብሬ ጋር አውልቄው የነበረው የአንገት ልብሴ ላይ ያርፋል።
ከክብሬ ጋር አውልቄው የነበረው ጃኬቴ ላይ ያርፋል።
ከክብሬ ጋር አውልቄው የነበረው ሱሬዬ ላይ ያርፋል።
በለቅሶዬ መሃል፣ "አይዞሽ... ሁሉም ያልፋል" የሚል ድምፅ ሰማሁና ዞርኩ። ከእኔ በእድሜ የምታንስ ልጅ ናት።
"ሁሉም ያልፋል" የሚል የታክሲ ጥቅስ አንብባ የምትደለለው ለዚያ ነው። ትንሽ ልጅ ስለሆነች፣ በቂ ስላልኖረች። አንዳንድ ነገሮች እንደኔ ላለው ሰው እንደማያልፍ የሚያስተምራት የህይወት ልምድ ስለሌላት፣ ቀልደኛ!
ዝም ብዬ አየሇትና በእሽታ ጭንቅላቴን ነቅንቄ ተመልሼ ወደ መስኮቱ ዞርኩ። ሁሉም ቢያልፍ ኖሮ ዛሬ እዚህ ታክሲ ውስጥ እያለቀስኩ ባልተቀመጥኩ፣ ሁሉም ቢያልፍ ኖሮ ለአምስት መቶ ብር አምስት መቶ ቦታ ባልተሰባበርኩ። ሁሉም ቢያልፍ ኖሮ እኔ ትርሲት የአቶ ከለላውና የወይዘሮ ሥምረት ሴት ልጅ፣ የብሌን ታላቅ እህት፣ የዳዊት ታናሽ እህት፣ የዳግም ፍቅረኛ ሀኜ በቀረሁ። አሁን ግን ትርሲት ሸለዋ ነኝ።
ሸሌ ነኝ፣ ሸሌ ብቻ።
ይህንን ሰውየው ዐይን ውስጥ ዐይቼዋለሁ። ይሄንን ሰውየው ትእዛዝ ውስጥ ሰምቼዋለሁ። ይህንን ሰውየው፣ "በሩን በደንብ ዝጊው" ንግግር ውስጥ አድምጭዋለሁ።
ሸሌ ነኝ።
ለማንበብ ደቂቃ የሚፈጅ ሥም በመስጠት የ'ኔን ሥራ ቅዱስ ማድረግ አይቻልምና፣ የለም፣ አንቺ እኮ 'በወሲብ ንግድ የተሰማራች ሴት' ነሽ!" ብላችሁ አታፅናኑኝ።
ከዛሬ ጀምሮ ሸሌ ነኝ።
በረሀብ እያዛጋሁ ቤቴ ገባሁና ከሰል አቀጣጠልኩ። ሳልበላ ውሃ ላፈላ። ሳልበላ በፈላ ውሃ ልታጠብ። ሳልበላ በፈላ ውሃ ገላዬን ልታጠብ። ሸሌነቴን በፈላ ውሃ ሙልጭ አድርጌ ልታጠብ።
ውሃው እስኪፈላ፣ ልብሶቼን አውልቄ ከሌሎቹ ልብሶቼ ጋር እንዳይቀላቀሉ በቤቴ አንዷ መአዘን ላይ ሰብስቤ ጣልኳቸው። ብዙ ልብስ የለኝም፤ ግን እነዚህን ልብሶች መልሼ የምለብሳቸው አይመስለኝም።
'ራቁቴን የሰመጠች አልጋዬ ላይ ቁጭ ብዬ ውሃው እስኪፈላ እየጠበቅኩ ቤቴን ዐየሁት። ለሰው የሚነገር ነገር ስለሌለኝ እንትኑ እዚያ ጋር፣ እትኑ ደግሞ እዛ ጋር አለ ብዬ ላወራችሁ አልፈልግም። በዋጋ ከተሰላ፤ አሁን ያለኝ፣ ዋጋ የከፈልኩበት አምስት መቶ ብር ብቻ ነው። አልጋዬ ላይ የተቀመጠው አምስት መቶ ብር።
ምንአልባት ካልገመታችሁ፣ እንዲህ ያለው ዋጋ ያልከፈልኩበት ብር ለማግኘት ሞክሬ ነበር። ማለቴ ዘልዬ ሸሌ አልሆንኩም። አሳጥሬ ልንገራችሁ። ሁሉንም ሥራ ሰርቻለው። ግን እኔንና እኔን የሚጠብቁ ቤተሰቦቼን ሆድ ፀጥ የሚያደርግ፣ አንገት ቀና የሚያደርግ፣ ደረት አስነፍቶ የሚያስኬድ ሥራ አላገኘሁም።
እውነቴን ነው የምላችሁ፣ እንጀራ ፍለጋ ሴት የሆንኩት ሰው ሆኜ ስላልተሳካልኝ ነው።
ልድገመው፣ እንጀራ ፍለጋ ሴት የሆንኩት ሰው ሆኜ ስላልተሳካልኝ ነው።
የሥጋ ለሥጋን ኑሮ የመረጥኩት ሌላ ነገር ሆኜ መኖር ስላልቻልኩ ነው። ለምሳሌ የሆነ ሰሞን የሆነ "ኤን ጂ ኦ" ሸሌ የመሆን አዝማሚያ ያሳየነውንም፣ ገብተው የተንቧቹበትንም ሴቶች ሰበሰበና፣ "ከዚህ አስነዋሪና ቆሻሻ ሥራ ነፃ እናውጣችሁ፣....ያልገባችሁትንም እናድናችሁ" አለን።
"አልጋ አንጣፊ ስለሆነች ከአልጋ ለመውደቅ ቅርብ ነች" ብለው ነው መሰለኝ፣ ፕሮጀክቱ ውስጥ አስገቡኝ። ደስ ብሎኝ ገባሁ። ኤን ጂ ኦው፣ "አማራጭ የገቢ ማግኛ ዘዴዎች" በሚል ለግማሻችን ጥልፍ፣ ለግማሻችን ዳንቴል ስራ አስተምሮ፤ "በሉ እንግዲህ ሂዱና ንፁህ ስራችሁን እየሰራችሁ በብልፅግና ኑሮ" ብሎ አንድ ኮንቴነር ቤት ተከራይቶልን ሄደ።
እኔ ከጥልፎቹ መሀል ነበርኩ። እንደተማርኩት እየጠለፍኩ አዲሱንና ንፁሑን ሥራዬን ነጻ መውጫዬ፣ መልካም እጣ ፈንታዬ፣ የእግዜር ካሳዬ አድርጌ ተቀብዬው ሥራ ጀምሬ ነበር።
ብዙዎቻችሁ፣ " እንዴ ሸሌ የሆነች ወይ ለመሆን ያኮበኮበች ሴት ሁሌም ሸሌ ናት" ብላችሁ እንደምታስቡ አውቃለሁ። "በሚኒ ስከርት መንገድ መቆም የለመደች ሴት፣ በ'እስከ ጉልበት' የሥራ ቀሚስ ቢሮ መቀመጥ አትችልም ብላችሁ እንደምታምኑ ከውቃለሁ።
፡
፡
#በሕይወት_እምሻው
፡
"ነይ እዚህ ጋር ! ልብስሽን አውልቀሽ ውስጥ ሳትገቢ...ብርድ ልብሱ ላይ ተኚ" ሲለኝ፣ ልማድ ሆኖብኝ መግደርደር ዳድቶኝ ነበር።
ድሮ፤ ልጃገረድ እንዳለሁ ግዜ መሽኮርመም። ሰው እንጂ ሴት ያልሆኑኩ መስሎኝ፣ ሥጋ ሸጬ እንጀራ ልገዛ ያልመጣሁ መስሎኝ።
አንገቴን እንደሰበርኩ ወደ አልጋው ሄድኩ ሲያገኘኝ እሄድ እንደነበረው አይደለም አካሄዴ።ሰበር ሰካ የለውም፣ ዕዩኝ ዕዩኝ የለውም፣ ተገዝቶ ወደ ሚታረድበት ቦታ እንደሚሄድ በግ ነው አካሄዴ።
ገዥዬ የማያውቀኝ፣ ሰው ፊት ልብሴን ሳወልቅ የመጀመርያዬ እንጀሆነ አያውቅም።
ገዥዬ፣ በገንዘብ ተገዝቼ ከወንድ ለመተኛት ስመጣ የመጀመርያዬ እንደሆነ አያውቅም።
ገዥዬ፣ ለዚህ ስራ ድንግል እንደሆንኩ አያውቅም።
ልብሴን ማውለቅ ሳልጀምር እየፈራው፣ "ይቅርታ....መብራቱን ታጠፋው?" አልኩት።
ዞር ብሎ ዐየኝና፣ "ሃሃ...ሃ! ታሾፌያለሽ እንዴ.? ለምንድን ነው የማጠፋው...? አለኝ። ይስቃል።
ፈራሁ ብለው አያምንም። በሰቀቀን ዝም ብዬ ማውለቅ ጀመርኩ። የአልጋው ጫፍ ላይ ኩምትር እንዳልኩ ድንገት እስካሁን መኖሩን ያላወኩት ብርድ አንዘፈዘፈኝ። ሳል ጀመረኝ።
ይሄን ግዜ ሰውየው ዞር ብሎ ዐየኝና ፤ "ምነው.. ብርድ.. ቲቢ.. ምናምን አለብሽ እንዴ?" አለኝ።
"አይ...በርዶኝ ነው...አያመኝም...አሁን በርዶኝ ነው..." ብዬ ብርድ ልብስ ውስጥ ገባሁ።
"ኖኖ!...ከላይ ሁኚ...አትግቢ..." አለኝ ቶሎ ብሎ ፣ ቀጭን ትዛዝ ነበር።
እምቢ ብዬ መሄድ እንደማልችል ማወቁ አስከፋኝ። እሺ ብዬው ስለመጣሁ እምቢ ብዬ ስለማልሄድ እርግጠኛ መሆኑን ሳውቅ ከፋኝ። ከነሳሌ ከብርድ ልብስ ወጣሁ። መጥቶ አጠገቤ ተኛ። ሰውነቴ በፍርሃት ተንዘፈዘፈ። ነውስጥ ሱሪ ብቻ ሲቀረው ዕርቃኑን ነው።
እግዜር በሚያውቀው፣ ከማላውቀው ሰው ቤት ለማደር መምጣት አልፈለግኩም ነበር።
የማላውቀው ሰው እጁቹን ጭኖቼ መሀል አስገብቶ እንዲፈነጭ አልፈለግኩም ነበር።
የማላውቀው ሰው ጆሮዬን ተጠግቶ እንዲያቃትትብኝ አልፈለግኩም ነበር። ግን ሰውየው አስገድዶ አላመጣኝም። አልደፈረኝም።
ያስገደደኝ ኑሮ ነው።
የደፈረኝ ድህነት ነው።
ሲነጋና ከኔ ጋር ያለውን ጣጣውን ሲጨርስ፣ የሰጠኝን አምስት መቶ አዳዳስ ብሮች እንደያዝኩ በትእዛዝ ያወለኩትን ልብሴን በከፍተኛ ፍጥነት ለበስኩ። ያወለኩት ክብሬ ግን አልጋው ላይ ቀርቷል።
"ቅዳሜ እመጣለሁ....ማን ብዬ ላስጠራሽ ?" አለኝ በተኛበት።
እንድሄድ ፈልጓል። አገልግሎቴ አብቅቷል። አሁን እንደተፋቀ የሞባይል ካርድ ነኝ። አሁን እንደተጫረ የክብሪት ዕንጨት ነኝ። በድጋሚ በጉጉት የሚያየኝ በሚቀጥለው ቅዳሜ መጥቼ እፎይ ማለት ሲያምረው ነው። ስሜን ነግሬው ዞር አልኩና ቦርሳዬን አንጠልጥዬ ለመሄድ ስዞር፣
"ማነሽ...እ...በሩን በደንብ ዝጊው!" አለኝ፣ አልጋው ላይ ተገላብጦ ጀርባውን እየሰጠኝ። ፊት እንኳን የማይገባኝ ሰው መሆኔን ሲነግረኝ ነው በጀርባው የሚያናግረኝ፣ የሚታወስ ሰም እንደሌለኝ ሲነግረኝ ነው ማነሽ ያለኝ።
ይሄን ሳስብ ተዛባሁ፣ ተዛነፍኩ።
ካለ አጥንት እንደተፈጠረ ሰው ሰውነቴ ለመቆምም ለመሄድም እምቢ እያለ ወደ ታክሲ ተራው ሄድኩ። ተኝቶ የነጋለት ሰው ይተራመሳል።
ታክሲው ውስጥ ገብቼ መስኮቱን ደገፍ አልኩና ያለ እቅድ ስቅስቅ ብዬ ማልቀስ ጀመርኩ። ከዐይኔ ግድብ የሚፈሰው እንባ ጉንጬቼ ላይ የሚያደርቅ ሳይሆን አዋሽ ወንዝ ለመግባት ያልም ይመስል ይንዠቀዠቃል።
ከክብሬ ጋር አውልቄው የነበረው የአንገት ልብሴ ላይ ያርፋል።
ከክብሬ ጋር አውልቄው የነበረው ጃኬቴ ላይ ያርፋል።
ከክብሬ ጋር አውልቄው የነበረው ሱሬዬ ላይ ያርፋል።
በለቅሶዬ መሃል፣ "አይዞሽ... ሁሉም ያልፋል" የሚል ድምፅ ሰማሁና ዞርኩ። ከእኔ በእድሜ የምታንስ ልጅ ናት።
"ሁሉም ያልፋል" የሚል የታክሲ ጥቅስ አንብባ የምትደለለው ለዚያ ነው። ትንሽ ልጅ ስለሆነች፣ በቂ ስላልኖረች። አንዳንድ ነገሮች እንደኔ ላለው ሰው እንደማያልፍ የሚያስተምራት የህይወት ልምድ ስለሌላት፣ ቀልደኛ!
ዝም ብዬ አየሇትና በእሽታ ጭንቅላቴን ነቅንቄ ተመልሼ ወደ መስኮቱ ዞርኩ። ሁሉም ቢያልፍ ኖሮ ዛሬ እዚህ ታክሲ ውስጥ እያለቀስኩ ባልተቀመጥኩ፣ ሁሉም ቢያልፍ ኖሮ ለአምስት መቶ ብር አምስት መቶ ቦታ ባልተሰባበርኩ። ሁሉም ቢያልፍ ኖሮ እኔ ትርሲት የአቶ ከለላውና የወይዘሮ ሥምረት ሴት ልጅ፣ የብሌን ታላቅ እህት፣ የዳዊት ታናሽ እህት፣ የዳግም ፍቅረኛ ሀኜ በቀረሁ። አሁን ግን ትርሲት ሸለዋ ነኝ።
ሸሌ ነኝ፣ ሸሌ ብቻ።
ይህንን ሰውየው ዐይን ውስጥ ዐይቼዋለሁ። ይሄንን ሰውየው ትእዛዝ ውስጥ ሰምቼዋለሁ። ይህንን ሰውየው፣ "በሩን በደንብ ዝጊው" ንግግር ውስጥ አድምጭዋለሁ።
ሸሌ ነኝ።
ለማንበብ ደቂቃ የሚፈጅ ሥም በመስጠት የ'ኔን ሥራ ቅዱስ ማድረግ አይቻልምና፣ የለም፣ አንቺ እኮ 'በወሲብ ንግድ የተሰማራች ሴት' ነሽ!" ብላችሁ አታፅናኑኝ።
ከዛሬ ጀምሮ ሸሌ ነኝ።
በረሀብ እያዛጋሁ ቤቴ ገባሁና ከሰል አቀጣጠልኩ። ሳልበላ ውሃ ላፈላ። ሳልበላ በፈላ ውሃ ልታጠብ። ሳልበላ በፈላ ውሃ ገላዬን ልታጠብ። ሸሌነቴን በፈላ ውሃ ሙልጭ አድርጌ ልታጠብ።
ውሃው እስኪፈላ፣ ልብሶቼን አውልቄ ከሌሎቹ ልብሶቼ ጋር እንዳይቀላቀሉ በቤቴ አንዷ መአዘን ላይ ሰብስቤ ጣልኳቸው። ብዙ ልብስ የለኝም፤ ግን እነዚህን ልብሶች መልሼ የምለብሳቸው አይመስለኝም።
'ራቁቴን የሰመጠች አልጋዬ ላይ ቁጭ ብዬ ውሃው እስኪፈላ እየጠበቅኩ ቤቴን ዐየሁት። ለሰው የሚነገር ነገር ስለሌለኝ እንትኑ እዚያ ጋር፣ እትኑ ደግሞ እዛ ጋር አለ ብዬ ላወራችሁ አልፈልግም። በዋጋ ከተሰላ፤ አሁን ያለኝ፣ ዋጋ የከፈልኩበት አምስት መቶ ብር ብቻ ነው። አልጋዬ ላይ የተቀመጠው አምስት መቶ ብር።
ምንአልባት ካልገመታችሁ፣ እንዲህ ያለው ዋጋ ያልከፈልኩበት ብር ለማግኘት ሞክሬ ነበር። ማለቴ ዘልዬ ሸሌ አልሆንኩም። አሳጥሬ ልንገራችሁ። ሁሉንም ሥራ ሰርቻለው። ግን እኔንና እኔን የሚጠብቁ ቤተሰቦቼን ሆድ ፀጥ የሚያደርግ፣ አንገት ቀና የሚያደርግ፣ ደረት አስነፍቶ የሚያስኬድ ሥራ አላገኘሁም።
እውነቴን ነው የምላችሁ፣ እንጀራ ፍለጋ ሴት የሆንኩት ሰው ሆኜ ስላልተሳካልኝ ነው።
ልድገመው፣ እንጀራ ፍለጋ ሴት የሆንኩት ሰው ሆኜ ስላልተሳካልኝ ነው።
የሥጋ ለሥጋን ኑሮ የመረጥኩት ሌላ ነገር ሆኜ መኖር ስላልቻልኩ ነው። ለምሳሌ የሆነ ሰሞን የሆነ "ኤን ጂ ኦ" ሸሌ የመሆን አዝማሚያ ያሳየነውንም፣ ገብተው የተንቧቹበትንም ሴቶች ሰበሰበና፣ "ከዚህ አስነዋሪና ቆሻሻ ሥራ ነፃ እናውጣችሁ፣....ያልገባችሁትንም እናድናችሁ" አለን።
"አልጋ አንጣፊ ስለሆነች ከአልጋ ለመውደቅ ቅርብ ነች" ብለው ነው መሰለኝ፣ ፕሮጀክቱ ውስጥ አስገቡኝ። ደስ ብሎኝ ገባሁ። ኤን ጂ ኦው፣ "አማራጭ የገቢ ማግኛ ዘዴዎች" በሚል ለግማሻችን ጥልፍ፣ ለግማሻችን ዳንቴል ስራ አስተምሮ፤ "በሉ እንግዲህ ሂዱና ንፁህ ስራችሁን እየሰራችሁ በብልፅግና ኑሮ" ብሎ አንድ ኮንቴነር ቤት ተከራይቶልን ሄደ።
እኔ ከጥልፎቹ መሀል ነበርኩ። እንደተማርኩት እየጠለፍኩ አዲሱንና ንፁሑን ሥራዬን ነጻ መውጫዬ፣ መልካም እጣ ፈንታዬ፣ የእግዜር ካሳዬ አድርጌ ተቀብዬው ሥራ ጀምሬ ነበር።
ብዙዎቻችሁ፣ " እንዴ ሸሌ የሆነች ወይ ለመሆን ያኮበኮበች ሴት ሁሌም ሸሌ ናት" ብላችሁ እንደምታስቡ አውቃለሁ። "በሚኒ ስከርት መንገድ መቆም የለመደች ሴት፣ በ'እስከ ጉልበት' የሥራ ቀሚስ ቢሮ መቀመጥ አትችልም ብላችሁ እንደምታምኑ ከውቃለሁ።
👍94❤10😁1
የራሳችሁ ጉዳይ
እኔ ግን በዛ ሰሞን እፎይታ ተሰምቶኝ ነበር።
ሳልጠፋ ስለተገኘሁ ደስ ብሎኝ ነበር።
ሸሌ መሆን የሚያጓጓኝ ሰሞን፣ የከጃጀለኝ ሰሞን አልጋ አንጣፌ ሆኜ የምሰራበት ቡና ቤት ውስጥ ያሉ የሚቀርቡኝ ሸሌዎችን ገድልና እሮሮ በታላቅ ትኩረት፣ በቀን በቀን እሰማ ነበር። ዐይ ነበር።
በመሸ ቁጥር፣ በ'ኮንደም አድርግ አታድርግ" ጭቅጭቅ፣ በጭንቅላቱ ሳይሆን በእንትኑ የሚያስብ ወንድ ጋር እየተጣሉ በፖሊስ መዳኘት አለ፣ በሚሉት የማስፈራራያ ወሬዎች ተሰላችቼ ነበር።
"በጥፊ ካልመታሁሽ ደስ አይለኝም!" እያለ፣ "ከላይም ከታችም ከሚደበድበኝ ወንድ ጋር አድሬ የከፈለኝን ገንዘብ በድብደባ ያበጠ ፊቴን ለመታከም ማዋሉ መረረኝ" በሚሉ ሴቶች ዋይታ ተማርሬ ነበር።
እሺ...ዝርዝሩ ይቅርባችሁ እና እንዲያው በደፈናው፣ በጨለመ ቁጥር ባለተራ ወንድ እላዬ ላይ ስለማይደፋደፍብኝ የእውነት ደስ ብሎኝ ነበር። ከዚህ እጣ ፈንታ ለጥቂት ስላመለጥኩ፣ ደስ ብሎኝ ነበር።
እናም፣ ቀን ቀን እየጋለ አቅልጦ እንደው ውሃ ሊያፈሰኝ በሚዳዳው ሙቀት፣ ሲመሽ ሲመሽ ጥፍር አውጥቶ ሰውነቴን በሚቦጫጭቅ ብርድ ሳልማረር፣ እዛች ኮንቴነር ውስጥ ቁጭ ብዬ ጥልፊን እጠልፍ ነበር።
በየወሩ፤ "አሁንስ በቃኝ...እንኳን ትርፍ ሊያመጣ ለሚያከስር ስራ ደግሞ!" እያሉ ከጥልፉም ከዳንቴሉም ጎራ ወጥተው ሸሌነትን የመረጡ፣ ወይም ወደ ሸሌነት የተመለሱ ጓደኞቼን እያየሁ እንኳን በንፅህና ጎዳና ለመቀጠል ብዙ ለፋሁ።
ብዙ ታተርኩ፣ ብዙ ወጣሁ፣ ብዙ ወረድኩ።
ንጹህ ስራዬ ግን ከሰው በታች አደረገኝ እንጂ ከፍ አላደረገኝም። ሱቄን የሚደጎበኙ ወንዶች ሁሉ፣ ጥልፍ የጠለፍኩበትን አልጋ ልብስ ከመግዛት ይልቅ እኔን ጠልፈው አልጋ ውስጥ ማስገባት ነበር የሚታትሩት። በአምስተኛው ወር የከሸፈውን ፕሮጀክት ተከትሎ የከሸፈውን ህልሜን ኮንቴነሩ ውስጥ ጥዬ ወደ "ሰጥቶ የመቀበል" አለም መጣሁ።
የዛሬው ሰውዬ የመጀመርያዬ ነበር።
"ሀ" ዬ አንደኛ ክፍሌ።
ሳልዋረድ መብላት ብፈልግም፣ ሳልገላመጥ መኖር ብሻም የሞከርኩት ሁሉ አልሳካ ብሎኝ ሸሌ ሆንኩ።ባላያችሁትና ባልኖራችሁት ሕይወቴ ፈርዳችሁብኝ ብትሰድቡና ብትረግሙኝም፣
ዓለም ስትፈጠር ገና ያኔ ከገበሬነት በፊት፣ ከአናጢነት በፊት፣ ከአስተማሪነት በፊት፣ ከምንም አይነት ሥራ በፊት፣ "ሲወርድና ሲዋረድ" እዚህ የደረሰውን ሥራዬ ግን በእርግማንና በስድብ ወጀብ ከምድረ ገፅ እንደማይጠፋ ታውቁታላችሁ
ምክንያቱም፣ በጨለማ ዝቅ ብዬ ያገኘሁት ገንዘብ እጄን የሚጠብቁ ቤተሰቦቼን ከፍ እንደሚያደርግልኝ አውቃለሁ።
ቀን የተጠየፉኝ ሰዎች ማታ እንደሚያመልኩኝ አውቃለሁ።
ቆሻሻው ስራዬ ንጹሕ እንጀራ እንደሚገዛ አውቃለሁ።
ስለዚህ፣ ወንድ ሊሆን የሚመጣን ወንድ ሴት ሆኜ እያስተናገድኩ እንደ ሰው እኖራለሁ። ሸሌ ነኝ።ከዛሬ ጀምሮ ሸሌ ነኝ።
✨አለቀ✨
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
እኔ ግን በዛ ሰሞን እፎይታ ተሰምቶኝ ነበር።
ሳልጠፋ ስለተገኘሁ ደስ ብሎኝ ነበር።
ሸሌ መሆን የሚያጓጓኝ ሰሞን፣ የከጃጀለኝ ሰሞን አልጋ አንጣፌ ሆኜ የምሰራበት ቡና ቤት ውስጥ ያሉ የሚቀርቡኝ ሸሌዎችን ገድልና እሮሮ በታላቅ ትኩረት፣ በቀን በቀን እሰማ ነበር። ዐይ ነበር።
በመሸ ቁጥር፣ በ'ኮንደም አድርግ አታድርግ" ጭቅጭቅ፣ በጭንቅላቱ ሳይሆን በእንትኑ የሚያስብ ወንድ ጋር እየተጣሉ በፖሊስ መዳኘት አለ፣ በሚሉት የማስፈራራያ ወሬዎች ተሰላችቼ ነበር።
"በጥፊ ካልመታሁሽ ደስ አይለኝም!" እያለ፣ "ከላይም ከታችም ከሚደበድበኝ ወንድ ጋር አድሬ የከፈለኝን ገንዘብ በድብደባ ያበጠ ፊቴን ለመታከም ማዋሉ መረረኝ" በሚሉ ሴቶች ዋይታ ተማርሬ ነበር።
እሺ...ዝርዝሩ ይቅርባችሁ እና እንዲያው በደፈናው፣ በጨለመ ቁጥር ባለተራ ወንድ እላዬ ላይ ስለማይደፋደፍብኝ የእውነት ደስ ብሎኝ ነበር። ከዚህ እጣ ፈንታ ለጥቂት ስላመለጥኩ፣ ደስ ብሎኝ ነበር።
እናም፣ ቀን ቀን እየጋለ አቅልጦ እንደው ውሃ ሊያፈሰኝ በሚዳዳው ሙቀት፣ ሲመሽ ሲመሽ ጥፍር አውጥቶ ሰውነቴን በሚቦጫጭቅ ብርድ ሳልማረር፣ እዛች ኮንቴነር ውስጥ ቁጭ ብዬ ጥልፊን እጠልፍ ነበር።
በየወሩ፤ "አሁንስ በቃኝ...እንኳን ትርፍ ሊያመጣ ለሚያከስር ስራ ደግሞ!" እያሉ ከጥልፉም ከዳንቴሉም ጎራ ወጥተው ሸሌነትን የመረጡ፣ ወይም ወደ ሸሌነት የተመለሱ ጓደኞቼን እያየሁ እንኳን በንፅህና ጎዳና ለመቀጠል ብዙ ለፋሁ።
ብዙ ታተርኩ፣ ብዙ ወጣሁ፣ ብዙ ወረድኩ።
ንጹህ ስራዬ ግን ከሰው በታች አደረገኝ እንጂ ከፍ አላደረገኝም። ሱቄን የሚደጎበኙ ወንዶች ሁሉ፣ ጥልፍ የጠለፍኩበትን አልጋ ልብስ ከመግዛት ይልቅ እኔን ጠልፈው አልጋ ውስጥ ማስገባት ነበር የሚታትሩት። በአምስተኛው ወር የከሸፈውን ፕሮጀክት ተከትሎ የከሸፈውን ህልሜን ኮንቴነሩ ውስጥ ጥዬ ወደ "ሰጥቶ የመቀበል" አለም መጣሁ።
የዛሬው ሰውዬ የመጀመርያዬ ነበር።
"ሀ" ዬ አንደኛ ክፍሌ።
ሳልዋረድ መብላት ብፈልግም፣ ሳልገላመጥ መኖር ብሻም የሞከርኩት ሁሉ አልሳካ ብሎኝ ሸሌ ሆንኩ።ባላያችሁትና ባልኖራችሁት ሕይወቴ ፈርዳችሁብኝ ብትሰድቡና ብትረግሙኝም፣
ዓለም ስትፈጠር ገና ያኔ ከገበሬነት በፊት፣ ከአናጢነት በፊት፣ ከአስተማሪነት በፊት፣ ከምንም አይነት ሥራ በፊት፣ "ሲወርድና ሲዋረድ" እዚህ የደረሰውን ሥራዬ ግን በእርግማንና በስድብ ወጀብ ከምድረ ገፅ እንደማይጠፋ ታውቁታላችሁ
ምክንያቱም፣ በጨለማ ዝቅ ብዬ ያገኘሁት ገንዘብ እጄን የሚጠብቁ ቤተሰቦቼን ከፍ እንደሚያደርግልኝ አውቃለሁ።
ቀን የተጠየፉኝ ሰዎች ማታ እንደሚያመልኩኝ አውቃለሁ።
ቆሻሻው ስራዬ ንጹሕ እንጀራ እንደሚገዛ አውቃለሁ።
ስለዚህ፣ ወንድ ሊሆን የሚመጣን ወንድ ሴት ሆኜ እያስተናገድኩ እንደ ሰው እኖራለሁ። ሸሌ ነኝ።ከዛሬ ጀምሮ ሸሌ ነኝ።
✨አለቀ✨
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍56😢18🔥10👎3👏2😁2❤1
💥💞#አልተዘዋወረችም💥💞
✍ አሌክስ አብርሃም
ክፍል አስራ ስምንት
አባቶች!
ንጹህና የሚቀዘቅዝ ክፍል ነበር፣ አብረን ከገባን በኋላ፣ አልጋ ላይ ተቀምጦ በእጁ አልጋውን መታ መታ እያደረገ ነይ እዚህ አለኝ፡፡ ቀስ ብዬ ሄጄ ተቀመጥኩ.. ይጣደፋል ክፉኛ ይጣደፋል፡፡ በበኩሌ በአጓጊ _ ሕልም ውስጥ እንዳለሁ ዓይነት ነገሮች ሁሉ ድንገት ባንኜ የሚቋረጡ እየመሰለኝ ነበር፡፡ በዝምታ አድርጊ የሚለኝን ሁሉ አደርጋለሁ፡፡ ጓጉቻለሁ፣ አውቃለሁ ምን እንደሚሆን፣ ጣቴን የምጠባ ሕፃን አይደለሁም፡፡ ከሆነም እዚህ ሰው ጋር መሆኑ የተለዬ ተአምር ነበር- ለእኔ፡፡ እንዲያውም በመኻል “አይ ይቅርብን' ብሎ ተነስቶ እንዳይሄድ እየፈራሁ ነበር፡፡ አጠቃላይ ለነገሩ አዲስ መሆኔና ድንገተኛ ነገር መሆኑ ከፈጠረብኝ መደነባበርና ጭንቀት ውጭ፣ ይኼ ሰው ምንም ቢያደርገኝ ምንም ቅሬታ አልነበረኝም፡፡ይኼ ቆንጆ ሰውዬ፣ ሀብታም ሰውዬ፣ ሳቂታ ሰውዬ፣ ቆንጆ ሚስት ያለችው ሰውዬ፣የሰፈሩ ሰው ሁሉ የሚያከብረው እና የሚወደው ሰውዬ፣ ምንድን ነው እኔ ጋር የሚሠራው “ጫማሽን አውልቂና ከፍ ብለሽ ተቀመጭ፣ አይዞሽ አትፍሪ"...እንዳለኝ አደረግሁ። ጉርድ ቀሚሴ ያጋለጠውን እግሬን እያዬ እና የሸሚዙን ቁልፍ እየፈታ... "ይኼ እግርሽ እንዴት እንደሚያምር ሰዎች አልነገሩሽም...'' አለኝ፡፡ አቀርቅሬ ዝም አልኩ፡፡ ሸሚዙን አውልቆ ወደ ጎን ወርወር አደረገና እጁን የተጋለጠ ጉልበቴ ላይ አሳረፈ ቀስ አድርጎ ወደ ራሱ ሳበኝ ... ደረቱ ላይ ተለጠፍኩ። እጁን ልኮ ከማነሳቼው ብዛት ለመቆንጠጥ እንኳን የሚያስቸግሩ ጡቶቼን ሲነካካኝ፣ ባለ በሌለ ኃይሌ ታፋዬን ገጥሜ ትንፋሼን ዋጥኩ፡፡ ልብሴን ቀስ በቀስ ሲያወልቅልኝ፣ በዝምታ ነበር የተባበርኩት፡፡ ተንጠራርቶ መብራቱን አጠፋው እፎይታ ተሰማኝ፡፡ አንሶላው ደስ የሚል ሽታ አለው፡፡ ከዚያ በኋላ የሆነው ሁሉ ፈጣንና ግራ አጋቢ ሕልም ነበር ሕመም፣ ደስታ፣ የማላውቀው ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ነበር የሚሰማኝ፡፡ በዓለም ላይ እንደ እኔ የሚፈቀር ሰው ያለ መስሎ አልተሰማኝም። ወንዶች ይጸዬፉኛል ብዬ አስብ ነበር፣ እንደዚህ ዓይነት ቆንጆ
ሀብታም፣ አገር ያደነቃት ውብ ሚስት ያለችው ሰውዬ ከንፈሬን፣ ጉንጨን፣ አንገቴን ሲስመኝ ዕንባዬ እየፈሰሰ በሁለት እጆቼ እስከቻልኩት ተጠምጥሜበት ሳላስበው? “ጋሽ ዓለምነህ'' አልኩት:: “ወይዬ! የኔ ጣፋጭ” እንዲሁ ነበር ያለኝ “የእኔ ጣፋጭ!"... “እግባኝ!” አልኩት። ጨለማ ነውና መልኩን ባላዬውም ትንታ ከምትመስል አተነፋፈሱ ሳቁ ያመለጠው ይመስለኛል። ዛሬ ላይ ሳስበው የሚያሳፍረኝም የሚያስቀኝም፣ ነገር ነው ይኼ... ቃሉ ራሱ “አግባኝ!'' ጨርሶ ሲነሳ መብራቱን አበራና የአልጋ ልብሱን ገልቦ የሆነ ነገር ተመለከተ፣ ሰውነቴን በእጄ ሸፈንኩ፡፡ “አመመሽ እንዴ?” “አይ! ደህና ነኝ!'” አልኩ እውነታው ግን፣ የሆነ ነገር ውስጤ የቀረ ዓይነት ኃይለኛ የማቃጠልና ታፋና ታፋዬ መገጣጠሚያ ላይ ሕመም እየተሰማኝ ነበር፡፡ “ሃሃሃሃ… የዛሬ ልጆች እሳቶች!'' እያለ ወደ ሻወር ገባ፡፡ ምን ማለት ነው እሳቶች!? ወደ ሻወር እንደገባ በፍጥነት አንሶላውን ገለጥኩና ሲባል የሰማሁትን ብር አምባር ነገር ፈለግሁ፡፡ አንሶላው ላይ ምንም ዓይነት ደም አልነበረም፤ የሆነ የተሳሳተ ነገር አለ? አልኩ ለራሴ፡፡ የሰማሁት እንደዚህ አልነበረም፣ ደም መኖር አለበት፣ ደም! ፊልሙ፣ መጽሐፉ፣ ወሬው ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲህ ዓይነት ነገር ያደረገች ሴት፣ ነጭ አንሶላ ጋር ትፋጠጣለች አላሉኝም፡፡ ከዚያ በፊት ወንድ የሚባል ባላውቅም፣ ምንም ደም አልነበረም፤ ጋሽ ዓለምነህ እንዳላመነኝ ያወቅሁት ቆይቶ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ ለወራት ነክቶኝ አያውቅም፡፡ እንዲያውም መንገድም ላይ ሲያዬን አልፎን ነበር የሚሄደው።
የሆነውን ሁሉ በውስጤ አፍኜ እንደገና ላዬው እጓጓ ነበር፡፡ እንዲያውም ይኼን ሁሉ ያደረገ እሱ እያለ ለዓይን ያስጠላችኝ ሚስቱ እትዬ ሆህተ ነበረች፡፡ ሳያት እና ለሁሉ ደግሞ ሁልጊዜ “እንደም? ዋልሽ? ሃይሚዬ” ትለኛለች፡፡ ልክ ባጠገቧ እንደ ዳልሁ። እንደ ማንም ሕፃን ነበር የምታዩኝ፡፡ በየኋት ቁጥር ወደ አእምሮዬ የሚመጠወ ልፍ ዓለምነህ ጋር አጉል ነገር እያደረጉ “የኔ ጠፋጬ!'” ሲላት ነው። ለመሆኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲተኙ ደም ዓይታ ይሆን? መሆን አለበት፣ እንዲህ እያልኩ አስባለሁ፡፡ እንዳንድ ማታ፣ ባልና ሚስቱ ተያይዘው በሰፈር ሲያልፉ፣ ምንም እንዳልተፈጠረ ሁለቱም ሰላም ይሉኛል፡፡ ታዲያ እፈራለሁ ድንገት እትዬ ሆሀተ ጠርታኝ “ሃይማኖት! የሚነግረኝ ነገር እውነት ነው ባሌ ጋር ተኝተሻል?'' የምትለኝ፣የምታሳስረኝ፣ ሰፈር ውስጥ የምታዋርደኝ፣ እንደዚያ እንደዚያ ዓይነት ሐሳብ ውስጤ እየገባ እንደ ብርድ ያንዘፈዝፈኛል፡፡
አንዴ ታዲያ ጋሽ ዓለምነህ ከትምህርት ቤት ስንመለስ አገኜንና፣ የተወውን መሸኜት ትዝ ያለው ይመስል ግቡ አለን፣ ገባን፡፡ ስለትምህርት ምናምን እያወራን ማኅደረን ሜክሲኮ አወረዳትና ብቻችንን ስንቀር ያለምንም ዙሪያ ጥምጥም ምን አለኝ ...
“ይች ...ቦይ ፍሬንድ አላት?''
"ማን?"
“ማኅደረ” ያላሰብኩት ጥያቄ:: “ኧረ! እኛ እንደዚህ ዓይነት ነገር አናውቅም'' “ሃሃሃ.. ያንችንማ አዬነው ...አሁን የሷን ንገሪኝ'' እንዳቀረቀርኩ “የላትም'' አልኩ፡፡ “ጥሩ! ነገ ከክላስ ስትወጡ፣ የሆነ ሰበብ ሰጥተሽ ብቻዋን እንድትሄድ አድርጊያት''
“구?” “ወደ ቤቷ ነዋ!'' አለ ቆጣ ብሎ፡፡ “እሺ!'' ነበር መልሴ፡፡ የዐሥረኛ ክፍል ቁጣ! በቀጣዩ ቀን ማኅደረን “ከትምህርት ቤት ስንመለስ ቤተክርስቲያን ፕሮግራም ስላለኝ አልጠብቅሽም” አልኳት፡፡ ቀደም ብዬ ስወጣ፣ ታክሲ መቆሚያው ጋር ከመድረሱ በፊት የጋሽ ዓለምነህ መኪና ቆማ አዬኋት። መንገዱን ተሻግሬ፣ በሩቁ አንድ የቆመ መኪና ኋላ ሰው የምጠብቅ መስዬ ቆምኩ። ማኅደረ ወደ ታክሲ መጠበቂያው አቀርቅራ ስትጣደፍ ጋሽ ዓለምነህ በቀስታ መኪናውን እያሽከረከረ ደረሰባትና ጠራት። የኋለኛውን በር ለመክፈት ሞክራ፣ ጎንበስ ብላ የሆነ ነገር ተናገረችና ወደ ከፈተላት የጋቢና በር ገባች፡፡ ውስጤ የቀረች ተስፋና መፈቀር ዕንባ ሆና ተንጠፈጠፈች፡፡ ወደ ጦር ኃይሎች ብረሪ ብረሪ አለኝ፡፡ ወደ ልደታ ፍርድ ቤት መሮጥ አማረኝ፣ ያቺን ሚስቱን “ባልሽ ማኅደረ ጋር ሊተኛ ይዟት ሄደ” ብሎ ነገር ማቀራቀር አማረኝ፡፡ ከታክሲ እንደወረድኩ እቤቴ አልሄድኩም፣ ልደታ እስኪወጣልኝ ተነፋረቅሁ፤ ቅናት አንገበገበኝ፡፡ ቤተክርስቲያን ገብቼ ወደ ማታ አካባቢ ማኅደረ በብስጭት ብው ብላ እቤት መጠች ፤ የማውቃት ማኅደረ አልነበረችም። “አንቺ! ያ ልክስክስ ሰውዬ ልሸኝሽ ብሎ አስገብቶ ጡቴን አልነካኝም መሰለሽ!'' ብላ ተአምር የነገረቺኝ ያኽል አፈጠጠችብኝ፡፡ “ማነው? አልኩ'' እንዳላወቀ፡፡
“ጋሽ ዓለምነህ ነዋ! ከሱ ብሎ ጋሽ!'' “ምን!? ይኼ ጨምላቃ! ጠርጥሬ ነበር” ብዬ አጋነንኩ እንደማያውቅ:: “አንቺማ ነግረሽኝ ነበር፣ እኔ ነኝ እንጂ ፉዞ፤ አሁኑኑ ሄጄ ለሚስቱ ነው የምነግራት... ነይ እንሂድ!” ብላ መንገድ ጀመረች፡፡ ከዚያም በፊት ከዚያም በኋላ ማኅደረ እንደዚያ ተቆጥታ ዓይቻት አላውቅም። “እንዴ! ቆይ የሆነውን ንገሪኝ እንጂ ከዚያ እንወስናለን'' አልኳት፡፡ “...ስወጣ አግኝቶ ልሸኝሽ አለኝ፣ እንዲያውም ሃይሚም የለችም ብቻዬን ከመሄድ ገላገለኝ ብዬ ደስ አለኝ። ከኋላ ልገባ ስል ጋቢና ግቢ አለኝ፣ አገር ሰላም ብዬ ዘው! ትንሽ እንደሄድን 'ዛሬ ብቻችንን ተገናኜኝ የኔ ቆንጆ' ብሎ በዛ ሰፌድ እጁ ጡቴን አላፈሰኝም መሰለሽ...
✍ አሌክስ አብርሃም
ክፍል አስራ ስምንት
አባቶች!
ንጹህና የሚቀዘቅዝ ክፍል ነበር፣ አብረን ከገባን በኋላ፣ አልጋ ላይ ተቀምጦ በእጁ አልጋውን መታ መታ እያደረገ ነይ እዚህ አለኝ፡፡ ቀስ ብዬ ሄጄ ተቀመጥኩ.. ይጣደፋል ክፉኛ ይጣደፋል፡፡ በበኩሌ በአጓጊ _ ሕልም ውስጥ እንዳለሁ ዓይነት ነገሮች ሁሉ ድንገት ባንኜ የሚቋረጡ እየመሰለኝ ነበር፡፡ በዝምታ አድርጊ የሚለኝን ሁሉ አደርጋለሁ፡፡ ጓጉቻለሁ፣ አውቃለሁ ምን እንደሚሆን፣ ጣቴን የምጠባ ሕፃን አይደለሁም፡፡ ከሆነም እዚህ ሰው ጋር መሆኑ የተለዬ ተአምር ነበር- ለእኔ፡፡ እንዲያውም በመኻል “አይ ይቅርብን' ብሎ ተነስቶ እንዳይሄድ እየፈራሁ ነበር፡፡ አጠቃላይ ለነገሩ አዲስ መሆኔና ድንገተኛ ነገር መሆኑ ከፈጠረብኝ መደነባበርና ጭንቀት ውጭ፣ ይኼ ሰው ምንም ቢያደርገኝ ምንም ቅሬታ አልነበረኝም፡፡ይኼ ቆንጆ ሰውዬ፣ ሀብታም ሰውዬ፣ ሳቂታ ሰውዬ፣ ቆንጆ ሚስት ያለችው ሰውዬ፣የሰፈሩ ሰው ሁሉ የሚያከብረው እና የሚወደው ሰውዬ፣ ምንድን ነው እኔ ጋር የሚሠራው “ጫማሽን አውልቂና ከፍ ብለሽ ተቀመጭ፣ አይዞሽ አትፍሪ"...እንዳለኝ አደረግሁ። ጉርድ ቀሚሴ ያጋለጠውን እግሬን እያዬ እና የሸሚዙን ቁልፍ እየፈታ... "ይኼ እግርሽ እንዴት እንደሚያምር ሰዎች አልነገሩሽም...'' አለኝ፡፡ አቀርቅሬ ዝም አልኩ፡፡ ሸሚዙን አውልቆ ወደ ጎን ወርወር አደረገና እጁን የተጋለጠ ጉልበቴ ላይ አሳረፈ ቀስ አድርጎ ወደ ራሱ ሳበኝ ... ደረቱ ላይ ተለጠፍኩ። እጁን ልኮ ከማነሳቼው ብዛት ለመቆንጠጥ እንኳን የሚያስቸግሩ ጡቶቼን ሲነካካኝ፣ ባለ በሌለ ኃይሌ ታፋዬን ገጥሜ ትንፋሼን ዋጥኩ፡፡ ልብሴን ቀስ በቀስ ሲያወልቅልኝ፣ በዝምታ ነበር የተባበርኩት፡፡ ተንጠራርቶ መብራቱን አጠፋው እፎይታ ተሰማኝ፡፡ አንሶላው ደስ የሚል ሽታ አለው፡፡ ከዚያ በኋላ የሆነው ሁሉ ፈጣንና ግራ አጋቢ ሕልም ነበር ሕመም፣ ደስታ፣ የማላውቀው ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ነበር የሚሰማኝ፡፡ በዓለም ላይ እንደ እኔ የሚፈቀር ሰው ያለ መስሎ አልተሰማኝም። ወንዶች ይጸዬፉኛል ብዬ አስብ ነበር፣ እንደዚህ ዓይነት ቆንጆ
ሀብታም፣ አገር ያደነቃት ውብ ሚስት ያለችው ሰውዬ ከንፈሬን፣ ጉንጨን፣ አንገቴን ሲስመኝ ዕንባዬ እየፈሰሰ በሁለት እጆቼ እስከቻልኩት ተጠምጥሜበት ሳላስበው? “ጋሽ ዓለምነህ'' አልኩት:: “ወይዬ! የኔ ጣፋጭ” እንዲሁ ነበር ያለኝ “የእኔ ጣፋጭ!"... “እግባኝ!” አልኩት። ጨለማ ነውና መልኩን ባላዬውም ትንታ ከምትመስል አተነፋፈሱ ሳቁ ያመለጠው ይመስለኛል። ዛሬ ላይ ሳስበው የሚያሳፍረኝም የሚያስቀኝም፣ ነገር ነው ይኼ... ቃሉ ራሱ “አግባኝ!'' ጨርሶ ሲነሳ መብራቱን አበራና የአልጋ ልብሱን ገልቦ የሆነ ነገር ተመለከተ፣ ሰውነቴን በእጄ ሸፈንኩ፡፡ “አመመሽ እንዴ?” “አይ! ደህና ነኝ!'” አልኩ እውነታው ግን፣ የሆነ ነገር ውስጤ የቀረ ዓይነት ኃይለኛ የማቃጠልና ታፋና ታፋዬ መገጣጠሚያ ላይ ሕመም እየተሰማኝ ነበር፡፡ “ሃሃሃሃ… የዛሬ ልጆች እሳቶች!'' እያለ ወደ ሻወር ገባ፡፡ ምን ማለት ነው እሳቶች!? ወደ ሻወር እንደገባ በፍጥነት አንሶላውን ገለጥኩና ሲባል የሰማሁትን ብር አምባር ነገር ፈለግሁ፡፡ አንሶላው ላይ ምንም ዓይነት ደም አልነበረም፤ የሆነ የተሳሳተ ነገር አለ? አልኩ ለራሴ፡፡ የሰማሁት እንደዚህ አልነበረም፣ ደም መኖር አለበት፣ ደም! ፊልሙ፣ መጽሐፉ፣ ወሬው ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲህ ዓይነት ነገር ያደረገች ሴት፣ ነጭ አንሶላ ጋር ትፋጠጣለች አላሉኝም፡፡ ከዚያ በፊት ወንድ የሚባል ባላውቅም፣ ምንም ደም አልነበረም፤ ጋሽ ዓለምነህ እንዳላመነኝ ያወቅሁት ቆይቶ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ ለወራት ነክቶኝ አያውቅም፡፡ እንዲያውም መንገድም ላይ ሲያዬን አልፎን ነበር የሚሄደው።
የሆነውን ሁሉ በውስጤ አፍኜ እንደገና ላዬው እጓጓ ነበር፡፡ እንዲያውም ይኼን ሁሉ ያደረገ እሱ እያለ ለዓይን ያስጠላችኝ ሚስቱ እትዬ ሆህተ ነበረች፡፡ ሳያት እና ለሁሉ ደግሞ ሁልጊዜ “እንደም? ዋልሽ? ሃይሚዬ” ትለኛለች፡፡ ልክ ባጠገቧ እንደ ዳልሁ። እንደ ማንም ሕፃን ነበር የምታዩኝ፡፡ በየኋት ቁጥር ወደ አእምሮዬ የሚመጠወ ልፍ ዓለምነህ ጋር አጉል ነገር እያደረጉ “የኔ ጠፋጬ!'” ሲላት ነው። ለመሆኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲተኙ ደም ዓይታ ይሆን? መሆን አለበት፣ እንዲህ እያልኩ አስባለሁ፡፡ እንዳንድ ማታ፣ ባልና ሚስቱ ተያይዘው በሰፈር ሲያልፉ፣ ምንም እንዳልተፈጠረ ሁለቱም ሰላም ይሉኛል፡፡ ታዲያ እፈራለሁ ድንገት እትዬ ሆሀተ ጠርታኝ “ሃይማኖት! የሚነግረኝ ነገር እውነት ነው ባሌ ጋር ተኝተሻል?'' የምትለኝ፣የምታሳስረኝ፣ ሰፈር ውስጥ የምታዋርደኝ፣ እንደዚያ እንደዚያ ዓይነት ሐሳብ ውስጤ እየገባ እንደ ብርድ ያንዘፈዝፈኛል፡፡
አንዴ ታዲያ ጋሽ ዓለምነህ ከትምህርት ቤት ስንመለስ አገኜንና፣ የተወውን መሸኜት ትዝ ያለው ይመስል ግቡ አለን፣ ገባን፡፡ ስለትምህርት ምናምን እያወራን ማኅደረን ሜክሲኮ አወረዳትና ብቻችንን ስንቀር ያለምንም ዙሪያ ጥምጥም ምን አለኝ ...
“ይች ...ቦይ ፍሬንድ አላት?''
"ማን?"
“ማኅደረ” ያላሰብኩት ጥያቄ:: “ኧረ! እኛ እንደዚህ ዓይነት ነገር አናውቅም'' “ሃሃሃ.. ያንችንማ አዬነው ...አሁን የሷን ንገሪኝ'' እንዳቀረቀርኩ “የላትም'' አልኩ፡፡ “ጥሩ! ነገ ከክላስ ስትወጡ፣ የሆነ ሰበብ ሰጥተሽ ብቻዋን እንድትሄድ አድርጊያት''
“구?” “ወደ ቤቷ ነዋ!'' አለ ቆጣ ብሎ፡፡ “እሺ!'' ነበር መልሴ፡፡ የዐሥረኛ ክፍል ቁጣ! በቀጣዩ ቀን ማኅደረን “ከትምህርት ቤት ስንመለስ ቤተክርስቲያን ፕሮግራም ስላለኝ አልጠብቅሽም” አልኳት፡፡ ቀደም ብዬ ስወጣ፣ ታክሲ መቆሚያው ጋር ከመድረሱ በፊት የጋሽ ዓለምነህ መኪና ቆማ አዬኋት። መንገዱን ተሻግሬ፣ በሩቁ አንድ የቆመ መኪና ኋላ ሰው የምጠብቅ መስዬ ቆምኩ። ማኅደረ ወደ ታክሲ መጠበቂያው አቀርቅራ ስትጣደፍ ጋሽ ዓለምነህ በቀስታ መኪናውን እያሽከረከረ ደረሰባትና ጠራት። የኋለኛውን በር ለመክፈት ሞክራ፣ ጎንበስ ብላ የሆነ ነገር ተናገረችና ወደ ከፈተላት የጋቢና በር ገባች፡፡ ውስጤ የቀረች ተስፋና መፈቀር ዕንባ ሆና ተንጠፈጠፈች፡፡ ወደ ጦር ኃይሎች ብረሪ ብረሪ አለኝ፡፡ ወደ ልደታ ፍርድ ቤት መሮጥ አማረኝ፣ ያቺን ሚስቱን “ባልሽ ማኅደረ ጋር ሊተኛ ይዟት ሄደ” ብሎ ነገር ማቀራቀር አማረኝ፡፡ ከታክሲ እንደወረድኩ እቤቴ አልሄድኩም፣ ልደታ እስኪወጣልኝ ተነፋረቅሁ፤ ቅናት አንገበገበኝ፡፡ ቤተክርስቲያን ገብቼ ወደ ማታ አካባቢ ማኅደረ በብስጭት ብው ብላ እቤት መጠች ፤ የማውቃት ማኅደረ አልነበረችም። “አንቺ! ያ ልክስክስ ሰውዬ ልሸኝሽ ብሎ አስገብቶ ጡቴን አልነካኝም መሰለሽ!'' ብላ ተአምር የነገረቺኝ ያኽል አፈጠጠችብኝ፡፡ “ማነው? አልኩ'' እንዳላወቀ፡፡
“ጋሽ ዓለምነህ ነዋ! ከሱ ብሎ ጋሽ!'' “ምን!? ይኼ ጨምላቃ! ጠርጥሬ ነበር” ብዬ አጋነንኩ እንደማያውቅ:: “አንቺማ ነግረሽኝ ነበር፣ እኔ ነኝ እንጂ ፉዞ፤ አሁኑኑ ሄጄ ለሚስቱ ነው የምነግራት... ነይ እንሂድ!” ብላ መንገድ ጀመረች፡፡ ከዚያም በፊት ከዚያም በኋላ ማኅደረ እንደዚያ ተቆጥታ ዓይቻት አላውቅም። “እንዴ! ቆይ የሆነውን ንገሪኝ እንጂ ከዚያ እንወስናለን'' አልኳት፡፡ “...ስወጣ አግኝቶ ልሸኝሽ አለኝ፣ እንዲያውም ሃይሚም የለችም ብቻዬን ከመሄድ ገላገለኝ ብዬ ደስ አለኝ። ከኋላ ልገባ ስል ጋቢና ግቢ አለኝ፣ አገር ሰላም ብዬ ዘው! ትንሽ እንደሄድን 'ዛሬ ብቻችንን ተገናኜኝ የኔ ቆንጆ' ብሎ በዛ ሰፌድ እጁ ጡቴን አላፈሰኝም መሰለሽ...
👍40❤4😢2