ማለት የእንግዳ እንግዳ መሆን ነው፡፡ እንግዳ ሆነን የሄድንባቼው ሰዎች በእንግድነት ሌሎች ሰዎች ቤት ይዘውን ቢሄዱ እንደማለት... እየሰማሽኝ ነው ማሂዬ? ብዥዥ... አለብኝ! ባሌ ይኽን ሲነግረኝ ከልቡ ነበር፡፡ ያ ሳቂታ ልጅ፣ እንዲህ ዓይነት የዘጠና ዓመት አሮጊት እንኳን የማትመረረውን ምሬት ከዬት አመጣው? መሸነፍ ዓይነት አለው... በሕይወት ስሸነፍ መጀመሪያ እጅ ወደ ላይ ስትለኝ፣ አንድ እጄን
አነሳሁ፤ የተነሳ እጄ ላይ ይኼ ባሌ ቀለበት አጠለቀ፤ ማግባቴ መማረክ ነበር። አልተማረኩም ለማለት የአንድ እጅ ምርኮ (መሽኮርመም ለምርኮም ይሠራል) ባለ መሸሻ መደበቂያዬ ስላልኳት አሜሪካ ይኼን ሲለኝ ግን ሁለተኛውንም እጄን ከፍ አድርጌ የተሟላ ምርኮኛ ሆንኩ። እጅሽን ስጭ አለኝ..አንድ እጄን አገሬ ለተወለደ ምሬት፣ ሌላኛውን ለፈረንጅ ምሬት የሰጠሁ ምርኮኛ ነኝ። ሁለት ተኩላ የሚናጠቃት ጠቦት፡፡ ቀሪው ጊዜ ምን ይሆን ብዬ አልሰጋም፤ እንደ ምርኮኛ የሚንከባከብ ባል አለኝ እንደማረከኝ ያላወቀ። የትም ከመውደቅ አይሻልም? ግን ምንድን ነው የትም? ማለቴ ጥሩ ሙያ ያውም ከነሥራ ልምዱ አለኝ፤ እንኳን ለራሴ ለሰው እተርፋለሁ፤ ምንድን ነበር አንቀልቅሎ ትዳር ውስጥ የሞጀረኝ? (መሞጄር የእኔ ቃል _ አይደለም፤ ከዚያ የተረገመ ልጅ የተጣበቀብኝ ቃል ነው...) "ይኼ ውሃ ይኼ ባሕር፣ ርቀቱ አይገባሽም፣ ርቀቱ አይገባኝም፣ ዝም ብለን እንሞጄር፤ እንስጠም ወይ እንንሳፈፍ፣ ከመሞጄር ብቻ አንስነፍ፤'' አብርሽ ጋር ፒዛ እየበላሁ ቡናውን እየጠጣ፣ ድንገት የአፍ መጥረጊያ ናብኪን አንስቶ በጥቁር እስክርቢቶ የጻፈው ግጥም ነው፣ እስካሁን እኔ ጋር አለ፡፡ ይኼው አብረን በተሞጀርንበት ባሕር እኔ ሰመጥኩ እሱ ተንሳፈፈ። የደራሲ ሥራ ሕይወትን መጋፈጥ ነው ወይስ በቃል አሸሞንሙኖ ማለፍ!?
የሆነ ሆኖ እንዴት ነው የምወደው? ቢያገባኝ ምን ይሆን ነበር? ልጅ ካልፈለገ፣ እንወልድም፤ ወሬ ካልፈለገ፣ አላወራም፤ ዘፈን ከጠላ፣ ዘፈን አልከፍትም፤ ..ግን ከሥራ ስመለስ የምወደው ሰው ወዳለበት ቤት ብሄድ ... በቃ ይሀችን ብቻ፤ ወደ እሱ ቤት ስሄድ እንደምደሰተው ወደዬቶም ስሄድ ተደስቼ አላውቅም፣ ሲጀመር ወደየትም ሄጄ አላውቅም፣ ወደሆነ ቦታ ስሸሽ ነው የኖርኩት፡፡ ወደ ሥራ የምሄደው ከቤቴ ለመሸሽ ነበር፣ ወደቤቴ የምሄደውም ከሥራ ለመሸሽ፤ ደስ ብሎኝ የምሄደው ለመሸሽ ሳይሆን ናፍቄው፣ ፈልጌው የምሄደው ወደ እሱ ብቻ ነበር...እሱ ጋር መድረስ፣ በክንዶቹ መኻል መታቀፍ፣ በከንፈሮቹ መሳም ብቻ አልነበረም ደስታዬ፣ መንገዱ ሁሉ ለእኔ ሐሴት ነበር፡፡ ስንት ቀን ታክሲ ላይ መልሴን ረስቼ ወረድኩ? የምናፍቀው ያንን ነው፣ ወደምወደው ቦታ መሄድ፤ አሟሟት ምረጭ ብባል ራሱ ወደምወደው ቦታ ሙዚቃ እየሰማሁ ስሄድ በመኻል ብሞት እላለሁ። “እና ምን አልሽ ማሂዬ ?'' ባለቤቴ ጠዬቀኝ፡፡ “እኔ እንጃ!''ትክ ብዬ አዬሁት፣ ሽበት ጸጉሩን ጀማምሮታል፣ ስንጋባ አልነበረውም፤ ቀለም ተቀብቶ ይሆናል። “ማለቴ እንደፈለክ፣ ለእኔ ችግር የለውም'' አልኩት፡፡ ዘሎ ተጠመጠመብኝና ግንባሬን፣ ጸጉሬን፣ ዓይኔን፣ አፍንጫዬን፣ ጉንጨን፣ ከንፈሬን ትርምስምስ አድርጎ ሳመኝ። ወደ አገሩ መግቢያ “ቪዛ” በእኔ ከንፈር የተመታለት ይመስል። ውስጤ ለባሌ ብሶት አላዘነም፣ ተስፋ ያደረኳት አሜሪካ፣ እያየኋት፣ እንደ አረፋ እጄ ላይ ስትጠፋ በግርምት ፈገግ አልኩ እንጂ፤ ጭራሽ ባል የሚባል ዕዳዋን ጣለችብኝ። ቀልድ የማያልቅባት ዓለም! እናም ባሌ እንዲህ አለ “ከዚህ የጧት ፀሐይ ከሚያስንቅ ፈገግታ እንዴት መራቅ ይቻላል?'' ደግሜ ፈገግ አልኩ፡፡ ገና ቅድም መብላት ያቆምኩትን ምግብ እንደገና ተያያዝኩት፤ ካገባሁ በኋላ ለራሴም እስኪገርመኝ በጣም በላተኛ ሆኜ ነበር፣ ምግብ የቀረበበት ሰሃን የታጠበ እስኪመስል አላቆምም።
“ማሂዬ ጣፍጦሻል መሰል የሆነ ነገር ይጨመርልሽ ...?'' “አዎ!...!'' አልኩ! ሆዳም ናት ብሎ ቢፈታኝ ምናለበት!? የት ሄድኩ እኔ?! እናትነት ርግማን ነው ምርቃት? ልጄን ሳያት ስንት ጊዜ አንጀቴ ተንሰፈሰፈ? ምን የሚያንሰፈስፍ ነገር አለ? አባቷ ከአሜሪካ ሰብስቦ ባመጣላት ድፍን የሰፈሩን ልጅ ማሳደግ በሚችል ልብስ ዘንጣ፣ ጡቴን ከጡጦ እያማረጠች ያማረ ግቢ ውስጥ በሰላምና በደስታ የምትኖር ልጅ፣ እናቷ መንገድ ዳር ጥላት እንደጠፋች አራስ የምታሳዝነኝ ለምንድነው? ትንንሽ እጆቿን አየር _ ላይ _ እያወራጨች ጣቶቿን እየጠባች፣ ከንፈሮቿ ላይ ውብ የማለዳ ጠል የመሰሉ የለሀጭ ጤዛዎች ሲንኳለሉ ስታምር!...ግን ታሳዝነኛለች፤የሆነ ነገር የበደልኳት ይመስለኛል፡፡ ካልራባት አታለቅስም፣ አትስቅም፣ ትንንሽ እጆቿን በባዶው አየር ላይ እያወራጨች ስትደክም የሆነ ቁም ነገር የምትሠራ ነው የምትመስለው፡፡ ዓይኖቼን ከዚህች ትንሽ ፍጥረት ላይ መንቀል አልችልም፡፡ እንዳፈጠጥኩባት ውዬ አድራለሁ፤ ባዬኋት ቁጥር የሆኑ ሰዎች በር አንኳኩተው፣ ልጅቷን አምጭ ብለው የሚወስዱብኝ ነው የሚመስለኝ። ስትተኛ ጠጋ ብዬ ትንፋሻዋን አዳምጣለሁ፤ ወይም በልብሷ ላይ በተነፈሰች ቁጥር ከፍ ዝቀ የሚል የደረቷን እንቅስቃሴ አያለሁ፡፡ “እንዴ! የእኔም ልጅ እኮ ናት ማሂ!'' ይላል አባቷ ሲያቅፋት ነፍሴም ዓይኔም ሲሸበር እያዬ። በእርግጥ የእርሱም ልጅ ናት ግን አስተቃቀፍ አይችልም፤ እንደ ትራስ ነው ድንገት ከአልጋ ላይ አንስቶ የሚያንጠለጥላት። ምንም ጥንቃቄ የሚባል ነገር የለዉም። ወንዶች ግን ምንድን ነው ችግራቼው? ሲያነሱም ሲጥሉም በደመነፍስ ነው? የሆነ ጊዜ ዳይፐር ላመጣ አንዴ ያዛት አልኩት፤ ወዲያው ጭርር ብላ ስታለቅስ ነፍሴን አላውቅም እጄ ላይ የያዝኩትን ሁሉ በታትኜው፣ ከእጁ ላይ ነጥቄ... “ምን አደረካት?" ብዬ ጮኽኩበት፡።
“ደህና ናት! በአጋጣሚ ይኼ ነገር ቧጭሯት ነው!” አለኝ፣ ግራ እጁ ላይ የሚያደርገውን አስቀያሚ ብራዝሌት' እያሳዬኝ፡፡ አንገቷ ላይ ደም የመሰለ ጭረት በረዥሙ ተጋድሞ ነበር። አበድኩበት! “ይኼን ነገር ወደዚያ አውልቅና ጣል!'' ብዬ ጮኽኩበት፡፡ “እኬ! ኦኬ! ማሂ ሶሪ!” ብሎ ወጥቶ ሄደ፡፡ ያ ቡጭሪያ እስከ አሁን ፈዛዛ ሆኖ መስመሩ አንገቷ ላይ አለ፡፡ የሚገርመው ብራዝሌቱምን ከእጁ ላይ አላወለቀውም። ሰው ቢሰማ ምን ይላል እንጂ፣ ይችን ፍጥረት : አባቷ እንደሚጋራኝ ሳስብ እናደዳለሁ፣ ስስት እላለሁ፡፡ማንም ጋር የማልጋራት የብቻዬ እንድትሆን ነው ፍላጎቴ። አባቷ፣ እናቷ፣ አያቷ፣ ምንጅላቷ፣ አክስቷ፣ አጎቷ እኔ ብቻ እንድሆን ነው ምኞቴ፡፡ ይዘሻት ጥፊ ጥፊ ይለኛል፡፡ ወደ ሆነ ሰው ወደማይኖርበት ዓለም፣ ወይም ሰው ወደሚኖርበት አራት ዓመት ስመላለስበት ወደኖርኩት ኮንዶሚኒዬም። ያ "ሲዲ ፕሌየር" ኦህህህ... እኔና አብርሽ ባልና ሚስት ሆነን ብንፋታ፣ ንብረት ክፍፍል ላይ ሁሉንም ነገር ውሰድ ያን “ሲዲ ፕሌየር" ብቻ ስጠኝ፣ እለው ነበር፡፡ ዛሬ ላይ ለዚያ ሲዲ ፕሌየር የነበረኝን ልዩ ፍቅር በጥልቀት ሳስበዉ እንዲሁ የእኔ ሙዚቃ ወዳድነት ከዚያ ቁስ ጋር የፈጠረው ግጥምጥሞሽ ብቻ እነዳልነበረ ገብቶኛል፡፡ አብረሃም በዚያ ሁሉ ጊዜ አንድም ቀን አፈቅርሻለሁ ብሎኝ አያዉቅም፤ አንድም ቀን! ስንተዋወቅ ስለ እግሬና ስለ ጠይምነቴ ከወረወራት አስተያዬት ውጭ ቆንጆ ነሽ ብሎኝ አያዉቅም፤ ነፍሴ ከምወደው ሰው አድናቆት ትፈልግ ነበር። እቤቱ በሄድኩ ቁጥር በወንድ የተዘፈነ የፍቅር ዘፈን እከፍታለሁ፤ በሲዲ ፕሌየሩ በኩል ከዘፋኙ የሚንቆረቆሩ የፍቅር ውዳሴዎችን ከሚስመኝ፣ ከሚያፈቀረኝ፣ ከሚዳስሰኝ፣ ከሚተኛኝ ከዚያ ሰው ለእኔ እንደሚነገሩ የፍቅር መወድሶች እያሰብኩ
አነሳሁ፤ የተነሳ እጄ ላይ ይኼ ባሌ ቀለበት አጠለቀ፤ ማግባቴ መማረክ ነበር። አልተማረኩም ለማለት የአንድ እጅ ምርኮ (መሽኮርመም ለምርኮም ይሠራል) ባለ መሸሻ መደበቂያዬ ስላልኳት አሜሪካ ይኼን ሲለኝ ግን ሁለተኛውንም እጄን ከፍ አድርጌ የተሟላ ምርኮኛ ሆንኩ። እጅሽን ስጭ አለኝ..አንድ እጄን አገሬ ለተወለደ ምሬት፣ ሌላኛውን ለፈረንጅ ምሬት የሰጠሁ ምርኮኛ ነኝ። ሁለት ተኩላ የሚናጠቃት ጠቦት፡፡ ቀሪው ጊዜ ምን ይሆን ብዬ አልሰጋም፤ እንደ ምርኮኛ የሚንከባከብ ባል አለኝ እንደማረከኝ ያላወቀ። የትም ከመውደቅ አይሻልም? ግን ምንድን ነው የትም? ማለቴ ጥሩ ሙያ ያውም ከነሥራ ልምዱ አለኝ፤ እንኳን ለራሴ ለሰው እተርፋለሁ፤ ምንድን ነበር አንቀልቅሎ ትዳር ውስጥ የሞጀረኝ? (መሞጄር የእኔ ቃል _ አይደለም፤ ከዚያ የተረገመ ልጅ የተጣበቀብኝ ቃል ነው...) "ይኼ ውሃ ይኼ ባሕር፣ ርቀቱ አይገባሽም፣ ርቀቱ አይገባኝም፣ ዝም ብለን እንሞጄር፤ እንስጠም ወይ እንንሳፈፍ፣ ከመሞጄር ብቻ አንስነፍ፤'' አብርሽ ጋር ፒዛ እየበላሁ ቡናውን እየጠጣ፣ ድንገት የአፍ መጥረጊያ ናብኪን አንስቶ በጥቁር እስክርቢቶ የጻፈው ግጥም ነው፣ እስካሁን እኔ ጋር አለ፡፡ ይኼው አብረን በተሞጀርንበት ባሕር እኔ ሰመጥኩ እሱ ተንሳፈፈ። የደራሲ ሥራ ሕይወትን መጋፈጥ ነው ወይስ በቃል አሸሞንሙኖ ማለፍ!?
የሆነ ሆኖ እንዴት ነው የምወደው? ቢያገባኝ ምን ይሆን ነበር? ልጅ ካልፈለገ፣ እንወልድም፤ ወሬ ካልፈለገ፣ አላወራም፤ ዘፈን ከጠላ፣ ዘፈን አልከፍትም፤ ..ግን ከሥራ ስመለስ የምወደው ሰው ወዳለበት ቤት ብሄድ ... በቃ ይሀችን ብቻ፤ ወደ እሱ ቤት ስሄድ እንደምደሰተው ወደዬቶም ስሄድ ተደስቼ አላውቅም፣ ሲጀመር ወደየትም ሄጄ አላውቅም፣ ወደሆነ ቦታ ስሸሽ ነው የኖርኩት፡፡ ወደ ሥራ የምሄደው ከቤቴ ለመሸሽ ነበር፣ ወደቤቴ የምሄደውም ከሥራ ለመሸሽ፤ ደስ ብሎኝ የምሄደው ለመሸሽ ሳይሆን ናፍቄው፣ ፈልጌው የምሄደው ወደ እሱ ብቻ ነበር...እሱ ጋር መድረስ፣ በክንዶቹ መኻል መታቀፍ፣ በከንፈሮቹ መሳም ብቻ አልነበረም ደስታዬ፣ መንገዱ ሁሉ ለእኔ ሐሴት ነበር፡፡ ስንት ቀን ታክሲ ላይ መልሴን ረስቼ ወረድኩ? የምናፍቀው ያንን ነው፣ ወደምወደው ቦታ መሄድ፤ አሟሟት ምረጭ ብባል ራሱ ወደምወደው ቦታ ሙዚቃ እየሰማሁ ስሄድ በመኻል ብሞት እላለሁ። “እና ምን አልሽ ማሂዬ ?'' ባለቤቴ ጠዬቀኝ፡፡ “እኔ እንጃ!''ትክ ብዬ አዬሁት፣ ሽበት ጸጉሩን ጀማምሮታል፣ ስንጋባ አልነበረውም፤ ቀለም ተቀብቶ ይሆናል። “ማለቴ እንደፈለክ፣ ለእኔ ችግር የለውም'' አልኩት፡፡ ዘሎ ተጠመጠመብኝና ግንባሬን፣ ጸጉሬን፣ ዓይኔን፣ አፍንጫዬን፣ ጉንጨን፣ ከንፈሬን ትርምስምስ አድርጎ ሳመኝ። ወደ አገሩ መግቢያ “ቪዛ” በእኔ ከንፈር የተመታለት ይመስል። ውስጤ ለባሌ ብሶት አላዘነም፣ ተስፋ ያደረኳት አሜሪካ፣ እያየኋት፣ እንደ አረፋ እጄ ላይ ስትጠፋ በግርምት ፈገግ አልኩ እንጂ፤ ጭራሽ ባል የሚባል ዕዳዋን ጣለችብኝ። ቀልድ የማያልቅባት ዓለም! እናም ባሌ እንዲህ አለ “ከዚህ የጧት ፀሐይ ከሚያስንቅ ፈገግታ እንዴት መራቅ ይቻላል?'' ደግሜ ፈገግ አልኩ፡፡ ገና ቅድም መብላት ያቆምኩትን ምግብ እንደገና ተያያዝኩት፤ ካገባሁ በኋላ ለራሴም እስኪገርመኝ በጣም በላተኛ ሆኜ ነበር፣ ምግብ የቀረበበት ሰሃን የታጠበ እስኪመስል አላቆምም።
“ማሂዬ ጣፍጦሻል መሰል የሆነ ነገር ይጨመርልሽ ...?'' “አዎ!...!'' አልኩ! ሆዳም ናት ብሎ ቢፈታኝ ምናለበት!? የት ሄድኩ እኔ?! እናትነት ርግማን ነው ምርቃት? ልጄን ሳያት ስንት ጊዜ አንጀቴ ተንሰፈሰፈ? ምን የሚያንሰፈስፍ ነገር አለ? አባቷ ከአሜሪካ ሰብስቦ ባመጣላት ድፍን የሰፈሩን ልጅ ማሳደግ በሚችል ልብስ ዘንጣ፣ ጡቴን ከጡጦ እያማረጠች ያማረ ግቢ ውስጥ በሰላምና በደስታ የምትኖር ልጅ፣ እናቷ መንገድ ዳር ጥላት እንደጠፋች አራስ የምታሳዝነኝ ለምንድነው? ትንንሽ እጆቿን አየር _ ላይ _ እያወራጨች ጣቶቿን እየጠባች፣ ከንፈሮቿ ላይ ውብ የማለዳ ጠል የመሰሉ የለሀጭ ጤዛዎች ሲንኳለሉ ስታምር!...ግን ታሳዝነኛለች፤የሆነ ነገር የበደልኳት ይመስለኛል፡፡ ካልራባት አታለቅስም፣ አትስቅም፣ ትንንሽ እጆቿን በባዶው አየር ላይ እያወራጨች ስትደክም የሆነ ቁም ነገር የምትሠራ ነው የምትመስለው፡፡ ዓይኖቼን ከዚህች ትንሽ ፍጥረት ላይ መንቀል አልችልም፡፡ እንዳፈጠጥኩባት ውዬ አድራለሁ፤ ባዬኋት ቁጥር የሆኑ ሰዎች በር አንኳኩተው፣ ልጅቷን አምጭ ብለው የሚወስዱብኝ ነው የሚመስለኝ። ስትተኛ ጠጋ ብዬ ትንፋሻዋን አዳምጣለሁ፤ ወይም በልብሷ ላይ በተነፈሰች ቁጥር ከፍ ዝቀ የሚል የደረቷን እንቅስቃሴ አያለሁ፡፡ “እንዴ! የእኔም ልጅ እኮ ናት ማሂ!'' ይላል አባቷ ሲያቅፋት ነፍሴም ዓይኔም ሲሸበር እያዬ። በእርግጥ የእርሱም ልጅ ናት ግን አስተቃቀፍ አይችልም፤ እንደ ትራስ ነው ድንገት ከአልጋ ላይ አንስቶ የሚያንጠለጥላት። ምንም ጥንቃቄ የሚባል ነገር የለዉም። ወንዶች ግን ምንድን ነው ችግራቼው? ሲያነሱም ሲጥሉም በደመነፍስ ነው? የሆነ ጊዜ ዳይፐር ላመጣ አንዴ ያዛት አልኩት፤ ወዲያው ጭርር ብላ ስታለቅስ ነፍሴን አላውቅም እጄ ላይ የያዝኩትን ሁሉ በታትኜው፣ ከእጁ ላይ ነጥቄ... “ምን አደረካት?" ብዬ ጮኽኩበት፡።
“ደህና ናት! በአጋጣሚ ይኼ ነገር ቧጭሯት ነው!” አለኝ፣ ግራ እጁ ላይ የሚያደርገውን አስቀያሚ ብራዝሌት' እያሳዬኝ፡፡ አንገቷ ላይ ደም የመሰለ ጭረት በረዥሙ ተጋድሞ ነበር። አበድኩበት! “ይኼን ነገር ወደዚያ አውልቅና ጣል!'' ብዬ ጮኽኩበት፡፡ “እኬ! ኦኬ! ማሂ ሶሪ!” ብሎ ወጥቶ ሄደ፡፡ ያ ቡጭሪያ እስከ አሁን ፈዛዛ ሆኖ መስመሩ አንገቷ ላይ አለ፡፡ የሚገርመው ብራዝሌቱምን ከእጁ ላይ አላወለቀውም። ሰው ቢሰማ ምን ይላል እንጂ፣ ይችን ፍጥረት : አባቷ እንደሚጋራኝ ሳስብ እናደዳለሁ፣ ስስት እላለሁ፡፡ማንም ጋር የማልጋራት የብቻዬ እንድትሆን ነው ፍላጎቴ። አባቷ፣ እናቷ፣ አያቷ፣ ምንጅላቷ፣ አክስቷ፣ አጎቷ እኔ ብቻ እንድሆን ነው ምኞቴ፡፡ ይዘሻት ጥፊ ጥፊ ይለኛል፡፡ ወደ ሆነ ሰው ወደማይኖርበት ዓለም፣ ወይም ሰው ወደሚኖርበት አራት ዓመት ስመላለስበት ወደኖርኩት ኮንዶሚኒዬም። ያ "ሲዲ ፕሌየር" ኦህህህ... እኔና አብርሽ ባልና ሚስት ሆነን ብንፋታ፣ ንብረት ክፍፍል ላይ ሁሉንም ነገር ውሰድ ያን “ሲዲ ፕሌየር" ብቻ ስጠኝ፣ እለው ነበር፡፡ ዛሬ ላይ ለዚያ ሲዲ ፕሌየር የነበረኝን ልዩ ፍቅር በጥልቀት ሳስበዉ እንዲሁ የእኔ ሙዚቃ ወዳድነት ከዚያ ቁስ ጋር የፈጠረው ግጥምጥሞሽ ብቻ እነዳልነበረ ገብቶኛል፡፡ አብረሃም በዚያ ሁሉ ጊዜ አንድም ቀን አፈቅርሻለሁ ብሎኝ አያዉቅም፤ አንድም ቀን! ስንተዋወቅ ስለ እግሬና ስለ ጠይምነቴ ከወረወራት አስተያዬት ውጭ ቆንጆ ነሽ ብሎኝ አያዉቅም፤ ነፍሴ ከምወደው ሰው አድናቆት ትፈልግ ነበር። እቤቱ በሄድኩ ቁጥር በወንድ የተዘፈነ የፍቅር ዘፈን እከፍታለሁ፤ በሲዲ ፕሌየሩ በኩል ከዘፋኙ የሚንቆረቆሩ የፍቅር ውዳሴዎችን ከሚስመኝ፣ ከሚያፈቀረኝ፣ ከሚዳስሰኝ፣ ከሚተኛኝ ከዚያ ሰው ለእኔ እንደሚነገሩ የፍቅር መወድሶች እያሰብኩ
👍33❤1
እራሴን ሳታልል ነው የኖርኩት፡፡ እሱ ጋር ተኝቼ ጆሮዎቼ ዘፈኖቹ ላይ ነበሩ፡፡ የራሴን ምኞት እንደ ፊልም እራሴ እያቀናበርኩ ሕይወቴን ሙሉ አድርጌ በገዛ ራሴ ሐሳብ
ሣልኩ፤ መለያየት ሲዘንብ የሕልም ሥዕሌን አቅፌ ተሰደድኩ፡፡ ያ የሙዚቃ ማጫወቻ ለሚያቅፈኝ አብረሃም የተባለ ሥጋ ነፍስ ነበር፡፡ ሁልጊዜ የማስበው ለእኔና ለልጄ የምትበቃ ትንሽ ቤት እከራያለሁ፣ ጥሩ ሞግዚት ቀጥሬ፣ ሥራዬን እየሠራሁ ብቻዬን እኖራለሁ፡፡ ትንሽ ቤት፣ ሰላምና ሙዚቃ ያለባት፣ እንግዳ የማይመጣባት፣ አክስት፣ አጎት፣ ምናምን የማይንኳተትባት... ባል የሚባል ሰው የሌለባት፣ በአካባቢው ጋራዥ የሚባል የሌለበት፣ ደራሲ የሚባል የማያልፍበት ነጻ ዓለም!! ዝም ብዬ ጡቴን ለዜማ እሰጣታለሁ፣ የጡቶቼ መተለቅ ይገርመኛል፡፡ ከማርገዜ በፊት ከነበራቼው መጠን አምስት እጥፍ ይሆናል ያደጉት፤ ይኼ ነገር ወተት ብቻ ነው? እላለሁ ለራሴ። ከወለድኩ በኋላ ሰውነቴም _ በማይታመን ፍጥነት ግልብጥብጡ ወጣ፡፡ ከውፍረቴ ብዛት ታፋና ታፋዬ ተጣብቆ፣ ስራመድ እየተፋተገ ደስ የማይል የማንጣጣት ስሜት ይፈጥርብኝ ነበር፡፡ ጉንጮቼ ድርፍጭ አሉ፣ የአንገቴ ነገርማ አይወራም፣ እንደ ዔሊ አንገት ተሰብስቦ የተደበቀ ነበር የሚመስለው፤ የአንገቴ መቀበር የማይታመን _ ነበር። _ ከሩቅ _ ለሚያዬኝ ሰው የሆነ የማይታይ ኃይል የለበስኩትን ‘ቲሸርት' ትከሻና ትከሻዬ ላይ በጣቶቹ ቆንጥጦ ወደ ላይ የሳበው ነበር የሚመስለው፡፡በሌ ሳሎን ተጎልቶ በቲቪ የሚያያቼውን የአሜሪካ ፉትቦል ተጨዋቾች መሰልኩ፡፡ እራሴን በመስተዋት እያዬሁ ማኅደረ ሰላም በሥጋ ማዕበል ተመታች እላለሁ። ከበፊት ልብሶቼ አንድ እንኳን ያልጠበበኝ አልነበረም። መጥበብማ የወግ ነው። ልብሶቼን ሳያቼው በዕድሜ እጥፍ የምበልጣት የታናሽ እህቴ ልብሶች ነበር የሚመስሉት፡፡ ስትወልጂ እርግፍ ነው የሚለው ቢሉኝም፣ ሰውነቴ በተለይም ቦርጨ “ቀሪ ልጅ አለ እንዴ?'' እስኪያስብል ከነበረበት ንቅንቅ አላለም፡፡ ከጎንና ጎኔ ተጣጥፎ ቁጭ የሚል ሥጋዬ፣ የለበስኩትን ብለብስ ፈጥጦ ይወጣል፤ በተለይ ስቀመጥ
ለራሴም ይገርመኝ ነበር። ልብስ መምረጥ ባል ከመምረጥ በላይ ሕይወቱን አስጨንቋታል፤ ምንም አያምርብኝም፡፡ አብዝቼ የምለብሰው ሰፋፊ ቲሸርቶችን' ነበር፡፡ “ጅም' ግቢና ስፖርት ጀምሪ አሉኝ በሕይወት ዘመኔ ዐሥር ሜትር ሩጨ የማላውቅ ልጅ፣ ሳስበው ገና ደከመኝ:: ሥጋዬን እንደ ልብስ አውልቀሽ ወደሆነ ቦታ ወርውሪው ይለኛል፡፡ በመስታዎች ራሴን ባዬሁ ቁጥር ብስጭት ውስጤን ይሞላዋል፡፡ ሥጋና ነፍስ እንዲህ ተጣልተው አያውቁም፡፡ ከምንም በላይ አልቅሽ አልቅሽ የሚለኝ ደግሞ ሆዴ ላይ (ከእንብርቴ ትንሽ ዝቅ ብሎ) እንደ ቦርጭ ያበጠውና ቆዳው የተዥጎረጎረው ነገር፡፡ ሁለቱም ታፋዬ ላይ ደግሞ በረዣዥሙ የወጣብኝ ሸንተር ነበር፡፡ ጥይምናዬ ያበሳጨው ምቀኛ ሰይጣን በሚያስጠላ ዥጉርጉር ቀለም በዘፈቀደ ያሰመረው መስመር ነበር የሚመስለው፡፡ መስመርማ የወግ ነው ከሩቅ ቆሞ ቀለም የረጨብኝ ነበር የሚመስለው፡፡ በተለይ ታፋዬ ላይ የወጣው እርከን መስሎ በደረጃ ተሰምሮ ለዓይን ይቀፋል፡፡ ሁሉም ነገር ሲያልፍ ነው መሰል የሚቆጨው፣ ስለጠይምነቴ አጋንነው ሲያወሩ ግዴለሸ ነኝ ብዬ አስብ ነበር፤ አሁን ላይ ግን በሸንተር የደፈረሰ ጠይምነቴ ያንገበግበኛል፡፡ ያልተቀባሁት የአገር ውስጥና የውጭ አገር ቅባት አልነበረም፤ እንዲያውም መስመሩ ደምቆ ወጣ፡፡ አንዳንዴ ታዲያ ምናለ እራቁቴን አንድ እንኳን ፎቶ ኖሮኝ በነበር እላለሁ፡፡ ለአንድ ዓመት የሥጋ ዘር በዞረበት ሳልዞር በምግብ ሞከርኩት፤ ቢተከል ሁለት ሄክታር መሬት የሚሸፍን ሰላጣ ፈጅቼ- ምንም ለወጥ አላመጣሁም። ባለቤቴ "ውፍረት'ኮ ጸጋ ነው፣ ደግሞ አንቺ ላይ ሲያምር” ይላል፡፡ አስተያዬቱ ግድ አይሰጠኝም፡፡ እንዲህ ሆኜ ያ ደደብ ቢያዬኝ እንደ በፊቱ ለጡቶቸ ይስገበገባል? እንደ በፊቱ ከእግር ጣቴ እስከ ራስ ጸጉሬ ልሳምሽ ይለኛል? እንደ በፊቱ...! በመጨረሻ የድሮ ፎቶዎቼን እያዬሁ “ደህና ሁኚ ማሂ'' ብዬ አለቀስኩ፡፡ አለቃቀሴ
ሙት የመሸኜት ዓይነት የመረረ ነበር፡፡ በአስክሬን ሳጥን ብቻ ሳይሆን በራስ ሥጋ መገነዝም አለ ለካ፡፡ የምወዳቼውን ልብሶች ሁሉ እነዚያን መጠለያዎቼን ለኔ ቢጤዎች እና በቅርብ ለተቀጠረች ሠራተኛዬ ሰጠሁ። አዳዲስ ልብሶቼ ሁሉ በእንግድነት ሄጀ የተጠለልኩባቼው የለቅሶ ቤት ድንኳኖች ይመስሉኛል፡፡ የዚያን ቀን አለቀስኩ፤ በራስ ሰውነት አለማዘዝ መቻል ያሳዝናል። ውፍረት ማለት የትም ሳይሄዱ የራስ ሰውነት ውስጥ መጥፋት ነው። አለ አይደል “የት ሄድኩ እኔ?'' ብሎ ራስን መጠየቅ፤ በቃ እንደዚያ ነው ስሜቱ። እንዲህ የእራሴ ስቃይ ሳያንሰኝ፣ ከአሜሪካ ለመጣ ሰው፣ ለብር ብላ ፍቅረኛዋን ፈነገለችው መባሉን ከጓደኛዬ ከሃይሚ ሰማሁ (የሚፈነግል ይፈንግላቼው) ሃይሚ እንደ በፊቱ ቶሎ ቶሎ አታዬኝም፣ ትናፍቀኝ ነበር፤ ናፍቆቱ ልክ እናቴ ትታን የጠፋት ሰሞን የሚሰማኝን ዓይነት ናፍቆት ነበር። ይሁን እና ሃይሚ _ እንደዚያ ጠፍታ በመጣች ቁጥር የምታወራኝ ወሬ ለቀናት ውስጤን ያንገበግበኛል፡፡ እሷ በየዋኅነት ብታወራቼውም፣ ወሬዎቹ ግን ቅስሜን የሚሰብሩ ነበሩ፡፡ ከሄደች በኋላ ሁልጊዜም አለቅሳለሁ። _ እንዳገባሁ ሰሞን የሚያውቀኝ ሁሉ በረዢም ምላሱ ትኩሱን የከሃዲነቴን ወሬ ለመቅመስ ተጋፋ ... ጨዋ መስላ ተባለ... ድሮስ አንገት ደፊ... ተባለ፣ ጀግና ናት ከዚች አገር በዬትም ብሎ መውጣት ነው ተባለ፡፡ እናንት የአገሬ ልጆች፣ ሕይወቴ የመረረ እኔን ተሰብስባችሁ እንደ አሞሌ ጨው የምትልሱኝ ስለምን ነው!?... ከብት ናችሁን....!? እንደቆዘምኩ ዓመታት ነጎዱ፡፡ ልጄ ዜማ ሁለት ዓመት ሞላት፡፡ አንድ ቀን በረንዳ ላይ ተቀምጨ ሰፊው ግቢ ውስጥ ድክ ድክ እያለች ከአበባ አበባ የሚበሩ ቢራቢሮዎችን የምታባርር ዜማን አያለሁ፡፡ ትልቅ ሥራ እንደሠራ ሰው እያለከለከች መጣች እና ዱባ የሚያካክሉ ጡቶቼን በትንንሽ እጆቿ ለመያዝ መታገል ጀመረች አቅፌ ጡት ሰጠኋት፣ እየጠባች እንቅልፍ ወሰዳት፡፡
የባሌ ቤተሰቦች ለእኔ አዝነው፤ ሁለት ዓመት ከጠባች በቃት እንግዲህ፤ ጸጉርሽም ተነቃቀለ'ኮ ይበቃታል ይሉኛል፡፡ እኔ ግን በጡት ሰበብ ከእቅፌ አለመውጣቷ ዓለሜ ነበር። ሰላም የማገኜው ዜማን አቅፊያት ቁጭ ስል ነበር፡፡ ሐሳቤ ይሰበሰባል፡፡ እንዴ መጥባት ካቆመች ይኼን ያኽል ጊዜ ታቅፋልኝ እንደማትቆይ አውቃለሁ፤ በቃ ከዚያ በኋላ የእኔ ብቻ አትሆንም፡፡ እንዲያውም ከእኔ ይልቅ የባሌ ቤተሰቦች በሚሠሩላት ምግብ፣ በሚያጫውቷት ጨዋታ፣ እየተሳበች ዞራ የምታዬኝ አይመስለኝም፡፡ ሙያ ለሌላት ድብርታም እናት ለማዘን ዕድሜዋ አይደለም። ወደምፈራው ባዶነትና ብቸኝነት መመለስ ያስፈራኛል፡፡ በቀስታ መኝታ ቤቷ ወስጄ አስተኝቻት በሰፊው የሳሎን መስኮት በኩል ቆምኩ፣ ምን እዚያ ወስዶ እንደገተረኝ እንጃ! ምንም አይታይም፤ የግቢው ረዥም የግንብ አጥር፣ ዛፎች እና ንጹህ ሰማይ...የተወለወለ የሚመስል ሰማያዊ! ሰማያዊ ቀለም እወዳለሁ፡፡ በመስኮት አሻግሬ እየተመለከትኩ። መሄድ ያምረኛል፤ መሄጃ የለኝም። ምን ዓይነት የተሳሳተ ሒሳብ ብሠራ ነው ሥራዬን፣ ቤተሰቦቼን፣ ጓደኛዬ ሃይሚን፣ አብርሽን እነዚህን የምወዳቸውን ነገሮች ሁሉ ትቼ ወደዚህ ትዳር ወደሚባል ጋግርታም ዓለም የተሰደድኩት? መሄጃወቼ እነዚህ ነበሩ። ሌላ ምን መሄጃ አለኝ? ድንገት እናቴን አስታወስሁ፣ ማስታወስ ስል ከሥር መሠረቱ፡፡ አእምሯችን እንዲህ ከርሞ ከርሞ ነገርን ከዚያና ከዚህ አሳክቶ የሚደርስበት እውነት የሚመስል ነገር አለ አይደል? እንደዚያ ነበር
ሣልኩ፤ መለያየት ሲዘንብ የሕልም ሥዕሌን አቅፌ ተሰደድኩ፡፡ ያ የሙዚቃ ማጫወቻ ለሚያቅፈኝ አብረሃም የተባለ ሥጋ ነፍስ ነበር፡፡ ሁልጊዜ የማስበው ለእኔና ለልጄ የምትበቃ ትንሽ ቤት እከራያለሁ፣ ጥሩ ሞግዚት ቀጥሬ፣ ሥራዬን እየሠራሁ ብቻዬን እኖራለሁ፡፡ ትንሽ ቤት፣ ሰላምና ሙዚቃ ያለባት፣ እንግዳ የማይመጣባት፣ አክስት፣ አጎት፣ ምናምን የማይንኳተትባት... ባል የሚባል ሰው የሌለባት፣ በአካባቢው ጋራዥ የሚባል የሌለበት፣ ደራሲ የሚባል የማያልፍበት ነጻ ዓለም!! ዝም ብዬ ጡቴን ለዜማ እሰጣታለሁ፣ የጡቶቼ መተለቅ ይገርመኛል፡፡ ከማርገዜ በፊት ከነበራቼው መጠን አምስት እጥፍ ይሆናል ያደጉት፤ ይኼ ነገር ወተት ብቻ ነው? እላለሁ ለራሴ። ከወለድኩ በኋላ ሰውነቴም _ በማይታመን ፍጥነት ግልብጥብጡ ወጣ፡፡ ከውፍረቴ ብዛት ታፋና ታፋዬ ተጣብቆ፣ ስራመድ እየተፋተገ ደስ የማይል የማንጣጣት ስሜት ይፈጥርብኝ ነበር፡፡ ጉንጮቼ ድርፍጭ አሉ፣ የአንገቴ ነገርማ አይወራም፣ እንደ ዔሊ አንገት ተሰብስቦ የተደበቀ ነበር የሚመስለው፤ የአንገቴ መቀበር የማይታመን _ ነበር። _ ከሩቅ _ ለሚያዬኝ ሰው የሆነ የማይታይ ኃይል የለበስኩትን ‘ቲሸርት' ትከሻና ትከሻዬ ላይ በጣቶቹ ቆንጥጦ ወደ ላይ የሳበው ነበር የሚመስለው፡፡በሌ ሳሎን ተጎልቶ በቲቪ የሚያያቼውን የአሜሪካ ፉትቦል ተጨዋቾች መሰልኩ፡፡ እራሴን በመስተዋት እያዬሁ ማኅደረ ሰላም በሥጋ ማዕበል ተመታች እላለሁ። ከበፊት ልብሶቼ አንድ እንኳን ያልጠበበኝ አልነበረም። መጥበብማ የወግ ነው። ልብሶቼን ሳያቼው በዕድሜ እጥፍ የምበልጣት የታናሽ እህቴ ልብሶች ነበር የሚመስሉት፡፡ ስትወልጂ እርግፍ ነው የሚለው ቢሉኝም፣ ሰውነቴ በተለይም ቦርጨ “ቀሪ ልጅ አለ እንዴ?'' እስኪያስብል ከነበረበት ንቅንቅ አላለም፡፡ ከጎንና ጎኔ ተጣጥፎ ቁጭ የሚል ሥጋዬ፣ የለበስኩትን ብለብስ ፈጥጦ ይወጣል፤ በተለይ ስቀመጥ
ለራሴም ይገርመኝ ነበር። ልብስ መምረጥ ባል ከመምረጥ በላይ ሕይወቱን አስጨንቋታል፤ ምንም አያምርብኝም፡፡ አብዝቼ የምለብሰው ሰፋፊ ቲሸርቶችን' ነበር፡፡ “ጅም' ግቢና ስፖርት ጀምሪ አሉኝ በሕይወት ዘመኔ ዐሥር ሜትር ሩጨ የማላውቅ ልጅ፣ ሳስበው ገና ደከመኝ:: ሥጋዬን እንደ ልብስ አውልቀሽ ወደሆነ ቦታ ወርውሪው ይለኛል፡፡ በመስታዎች ራሴን ባዬሁ ቁጥር ብስጭት ውስጤን ይሞላዋል፡፡ ሥጋና ነፍስ እንዲህ ተጣልተው አያውቁም፡፡ ከምንም በላይ አልቅሽ አልቅሽ የሚለኝ ደግሞ ሆዴ ላይ (ከእንብርቴ ትንሽ ዝቅ ብሎ) እንደ ቦርጭ ያበጠውና ቆዳው የተዥጎረጎረው ነገር፡፡ ሁለቱም ታፋዬ ላይ ደግሞ በረዣዥሙ የወጣብኝ ሸንተር ነበር፡፡ ጥይምናዬ ያበሳጨው ምቀኛ ሰይጣን በሚያስጠላ ዥጉርጉር ቀለም በዘፈቀደ ያሰመረው መስመር ነበር የሚመስለው፡፡ መስመርማ የወግ ነው ከሩቅ ቆሞ ቀለም የረጨብኝ ነበር የሚመስለው፡፡ በተለይ ታፋዬ ላይ የወጣው እርከን መስሎ በደረጃ ተሰምሮ ለዓይን ይቀፋል፡፡ ሁሉም ነገር ሲያልፍ ነው መሰል የሚቆጨው፣ ስለጠይምነቴ አጋንነው ሲያወሩ ግዴለሸ ነኝ ብዬ አስብ ነበር፤ አሁን ላይ ግን በሸንተር የደፈረሰ ጠይምነቴ ያንገበግበኛል፡፡ ያልተቀባሁት የአገር ውስጥና የውጭ አገር ቅባት አልነበረም፤ እንዲያውም መስመሩ ደምቆ ወጣ፡፡ አንዳንዴ ታዲያ ምናለ እራቁቴን አንድ እንኳን ፎቶ ኖሮኝ በነበር እላለሁ፡፡ ለአንድ ዓመት የሥጋ ዘር በዞረበት ሳልዞር በምግብ ሞከርኩት፤ ቢተከል ሁለት ሄክታር መሬት የሚሸፍን ሰላጣ ፈጅቼ- ምንም ለወጥ አላመጣሁም። ባለቤቴ "ውፍረት'ኮ ጸጋ ነው፣ ደግሞ አንቺ ላይ ሲያምር” ይላል፡፡ አስተያዬቱ ግድ አይሰጠኝም፡፡ እንዲህ ሆኜ ያ ደደብ ቢያዬኝ እንደ በፊቱ ለጡቶቸ ይስገበገባል? እንደ በፊቱ ከእግር ጣቴ እስከ ራስ ጸጉሬ ልሳምሽ ይለኛል? እንደ በፊቱ...! በመጨረሻ የድሮ ፎቶዎቼን እያዬሁ “ደህና ሁኚ ማሂ'' ብዬ አለቀስኩ፡፡ አለቃቀሴ
ሙት የመሸኜት ዓይነት የመረረ ነበር፡፡ በአስክሬን ሳጥን ብቻ ሳይሆን በራስ ሥጋ መገነዝም አለ ለካ፡፡ የምወዳቼውን ልብሶች ሁሉ እነዚያን መጠለያዎቼን ለኔ ቢጤዎች እና በቅርብ ለተቀጠረች ሠራተኛዬ ሰጠሁ። አዳዲስ ልብሶቼ ሁሉ በእንግድነት ሄጀ የተጠለልኩባቼው የለቅሶ ቤት ድንኳኖች ይመስሉኛል፡፡ የዚያን ቀን አለቀስኩ፤ በራስ ሰውነት አለማዘዝ መቻል ያሳዝናል። ውፍረት ማለት የትም ሳይሄዱ የራስ ሰውነት ውስጥ መጥፋት ነው። አለ አይደል “የት ሄድኩ እኔ?'' ብሎ ራስን መጠየቅ፤ በቃ እንደዚያ ነው ስሜቱ። እንዲህ የእራሴ ስቃይ ሳያንሰኝ፣ ከአሜሪካ ለመጣ ሰው፣ ለብር ብላ ፍቅረኛዋን ፈነገለችው መባሉን ከጓደኛዬ ከሃይሚ ሰማሁ (የሚፈነግል ይፈንግላቼው) ሃይሚ እንደ በፊቱ ቶሎ ቶሎ አታዬኝም፣ ትናፍቀኝ ነበር፤ ናፍቆቱ ልክ እናቴ ትታን የጠፋት ሰሞን የሚሰማኝን ዓይነት ናፍቆት ነበር። ይሁን እና ሃይሚ _ እንደዚያ ጠፍታ በመጣች ቁጥር የምታወራኝ ወሬ ለቀናት ውስጤን ያንገበግበኛል፡፡ እሷ በየዋኅነት ብታወራቼውም፣ ወሬዎቹ ግን ቅስሜን የሚሰብሩ ነበሩ፡፡ ከሄደች በኋላ ሁልጊዜም አለቅሳለሁ። _ እንዳገባሁ ሰሞን የሚያውቀኝ ሁሉ በረዢም ምላሱ ትኩሱን የከሃዲነቴን ወሬ ለመቅመስ ተጋፋ ... ጨዋ መስላ ተባለ... ድሮስ አንገት ደፊ... ተባለ፣ ጀግና ናት ከዚች አገር በዬትም ብሎ መውጣት ነው ተባለ፡፡ እናንት የአገሬ ልጆች፣ ሕይወቴ የመረረ እኔን ተሰብስባችሁ እንደ አሞሌ ጨው የምትልሱኝ ስለምን ነው!?... ከብት ናችሁን....!? እንደቆዘምኩ ዓመታት ነጎዱ፡፡ ልጄ ዜማ ሁለት ዓመት ሞላት፡፡ አንድ ቀን በረንዳ ላይ ተቀምጨ ሰፊው ግቢ ውስጥ ድክ ድክ እያለች ከአበባ አበባ የሚበሩ ቢራቢሮዎችን የምታባርር ዜማን አያለሁ፡፡ ትልቅ ሥራ እንደሠራ ሰው እያለከለከች መጣች እና ዱባ የሚያካክሉ ጡቶቼን በትንንሽ እጆቿ ለመያዝ መታገል ጀመረች አቅፌ ጡት ሰጠኋት፣ እየጠባች እንቅልፍ ወሰዳት፡፡
የባሌ ቤተሰቦች ለእኔ አዝነው፤ ሁለት ዓመት ከጠባች በቃት እንግዲህ፤ ጸጉርሽም ተነቃቀለ'ኮ ይበቃታል ይሉኛል፡፡ እኔ ግን በጡት ሰበብ ከእቅፌ አለመውጣቷ ዓለሜ ነበር። ሰላም የማገኜው ዜማን አቅፊያት ቁጭ ስል ነበር፡፡ ሐሳቤ ይሰበሰባል፡፡ እንዴ መጥባት ካቆመች ይኼን ያኽል ጊዜ ታቅፋልኝ እንደማትቆይ አውቃለሁ፤ በቃ ከዚያ በኋላ የእኔ ብቻ አትሆንም፡፡ እንዲያውም ከእኔ ይልቅ የባሌ ቤተሰቦች በሚሠሩላት ምግብ፣ በሚያጫውቷት ጨዋታ፣ እየተሳበች ዞራ የምታዬኝ አይመስለኝም፡፡ ሙያ ለሌላት ድብርታም እናት ለማዘን ዕድሜዋ አይደለም። ወደምፈራው ባዶነትና ብቸኝነት መመለስ ያስፈራኛል፡፡ በቀስታ መኝታ ቤቷ ወስጄ አስተኝቻት በሰፊው የሳሎን መስኮት በኩል ቆምኩ፣ ምን እዚያ ወስዶ እንደገተረኝ እንጃ! ምንም አይታይም፤ የግቢው ረዥም የግንብ አጥር፣ ዛፎች እና ንጹህ ሰማይ...የተወለወለ የሚመስል ሰማያዊ! ሰማያዊ ቀለም እወዳለሁ፡፡ በመስኮት አሻግሬ እየተመለከትኩ። መሄድ ያምረኛል፤ መሄጃ የለኝም። ምን ዓይነት የተሳሳተ ሒሳብ ብሠራ ነው ሥራዬን፣ ቤተሰቦቼን፣ ጓደኛዬ ሃይሚን፣ አብርሽን እነዚህን የምወዳቸውን ነገሮች ሁሉ ትቼ ወደዚህ ትዳር ወደሚባል ጋግርታም ዓለም የተሰደድኩት? መሄጃወቼ እነዚህ ነበሩ። ሌላ ምን መሄጃ አለኝ? ድንገት እናቴን አስታወስሁ፣ ማስታወስ ስል ከሥር መሠረቱ፡፡ አእምሯችን እንዲህ ከርሞ ከርሞ ነገርን ከዚያና ከዚህ አሳክቶ የሚደርስበት እውነት የሚመስል ነገር አለ አይደል? እንደዚያ ነበር
👍40❤5
ይኼንኛው ሐሳቤ። እናቴ በመጥፋቷ ውስጤ ለረዠም ዓመታት አዝኖባት ነበር፡፡ ሌላ ወንድ ጋር መሄዷ አባባን የመካድ፣ እኛን ልጆቿን የመጸዬፍ ነገር አድርጌ ወስጄው ነበር፤ አባባ ይወዳታል፣ ያከበራታል። በሥርዓት ይሁን በመልክ፣ በትምህርት ይሁን በሌላው ወላጆች በልጆቻቼው ሊኮሩበት በሚገባ ነገር ሁሉ የምናኮራ ልጆች ነበርናት። ከዚህ በላይ ከሕይወት ምን ፈልጋ ሄደች? ይኼ ነበር የዓመታት ጥያቄዬ፡፡ በዚያች ቅጽበት ግን ጥያቄዬን በሌላ መንገድ እንደገና ጠዬቅሁ...አባባ ጥሩ ሰው ነው- ልክ እንደ ባሌ፡፡ እናቴን ይንከባከባት ነበር፤ ባሌ እኔን እንደሚንከባከበው፡፡ ያፈቅራት ነበር፤ባሌ እኔን እንደሚያፈቅረው፡፡ ግን እናቴ ይኼ ሁሉ ሳይበግራት
ምርጫዋን ተከትላ መንጎዷ ምን ዓይነት ጥንካሬ ቢኖራት ነው!?...ከሌላ ሰው ልጅ ወልዳለች ተብሏል፤ ምናይነት እናት ነው የምትሆነው? አባባን አታፍቅረው እሺ እኔም ባሌን አላፈቅረውም፣ ሌላ የምታፈቅረው ሰው ይኑር እኔም ሌላ ሰው ልቤ ውስጥ አለ ግን ከማላፈቅረው ሰው ብወልዳትም ልጄን ትቼ ከምሄድ ሞቴን እመርጣለሁ! እንዴት ያንን ቻለች? ዕድሜ ልኳን የልጆቿ ናፍቆት ቅጣት እንደሚሆንባት አልጠራጠርም፤ ግን ደግሞ ከማያፈቅሩት ጋር መኖርም ቅጣት ነው። የትኛውም ምቾት የትኛውም ክብርና እንክብካቤ የማይፈውሰው ባርነት፣ መሰሪያ የታጠቀ ወታደር በሩ ላይ ባይቆምም፣ ከፍቅር ውጭ በማንኛውም ሰበብ የተጣመሩበት ትዳር እስር ቤት ነው፤ መስኮት የእስረኛ ነፍስ መነፅር ሳይሆን ይቀራል? በቆምኩበት ቡና ይሼተኛል እናም ያቅለሸልሼኛል አውቀዋለሁ ስሜቱን ሁለተኛ አርግዣለሁ፡፡ ምንም የተለዬ ስሜት አልተሰማኝም፡፡ እንዲሁ ትውልድ የሚባል ነገር በውስጤ የሚያልፍብኝ ባዶ መተላለፊያ ነገር ከመሆን ስሜት ውጭ! ተመልሼ አልጋዬ ጫፍ ላይ ተቀመጥኩና ካለምንም ምክንያት ኮሜዲኖው ላይ የተቀመጡትን ቁልፎች አነሳሁ፡፡ ወደ አምስት የሚሆኑ በቁልፍ መያዣ ዘለበት የተሰኩ ቁልፎች ናቸው፤ የመኪና ቁልፍ የቤት ቁልፍ የካዝና ቁልፍ(እዚያ ካዝና ውስጥ ቁጥር ስፍር የሌላቼው የወርቅ ጌጣጌጦች(የዚህ የባሌ ስጦታ) እና የጋብቻ ዶክሜንቶች አሉ፡፡ ከእኔ በስተቀር ማንም የምን ቁልፍ እንደሆነ የማያውቀው አንድ መካከለኛ ቁልፍ የማንጠለጥላቼው ጥቂት ቁልፎች ጋር ሁሌም አለ። ለዓመታት አንጠልጥዬው ስዞር ማንም(ያው ማንም ባለቤቴ ነው) የምንድን ቁልፍ ነው? ብሎኝ አያውቅም። ጠባሳችን የት ላይ እንዳለ ከራሳችን በስተቀር ማን ያውቃል?! አብርሃም የሰጠኝ የቤቱ ቁልፍ ነበር። ምንም ነገር የለኝም፤ ፎቶው የለኝም፣ ሰጥቶኝ የሚያውቀው ስጦታ የለም፣ ከእርሱ የቀረኝ ብቼኛ ነገር የቤቱ ቁልፍ ነበር፡፡ ይኼ በእጄ ስይዘው እንደ አንዳች ነገር ሰላም የሚሰጠኝ ቁልፍ፤ ስንት ቀን ይኼን ቁልፍ በእጆቼ እያገላበጥኩ እንደ ተአምር አዬሁት? ስንቴ በሃሳብ ነጎድኩ!? ያንን የኮንዶሚኒዬም
የብረት በር ስከፍት ልቤ በደስታ ተመንጥቃ ልትወጣ ትደርስ ነበር። ከቀለበት እኩል የሆነ ቃልኪዳን ነገር ያለበት ቁልፍ ይመስለኛል፡፡ ባወጣ ባወርድ አልገለጥልሽ ያለኝ አንድ ነገር፣ አንዳንዴ ምክንያቱን ለራሳችን እንኳ በማይገባን ምክንያት ለቅርቦቻችን፣ ብዙ ለዋሉልን- ባይውሉልንም፣ ምንም ላልበደሉን ሰዎች ይሁዳ ሆነን አሳልፈን ለሐዘን ስንሰጣቼው፤ ሕይወታችንን ለመሳቀሉ ክፉዎች ግን፣ እንደ ክርስቶስ ካልተሰቀልንላችሁ ስንል የመገኜታችን ነገር ምን ይሆን ሚስጥሩ? ብስጭት ውስጤን ሞላው፤ ቁልፎቹ የተሰኩበትን ዘለበት ፈልቅቄ ያንን ቁልፍ ነጥዬ አወጣሁትና በብስጭት ወደ መፀዳጃ ቤት ገብቼ የሽንት ቤቱ መቀመጫ ውስጥ ወረወርኩት፡፡ ሸክላው ላይ ተቅጨልጭሎ ውሃው ውስጥ በእርጋታ ገብቶ ቁጭ አለ፤ የውሃ መልቀቂያውን ባለ በሌለ ኃይሌ ስጫነው ንጹህ ውሃ እየተዥጎደጎደ ቁልቁል ጎርፎ ሲያልቅ ቁልፉ ከመዓበል በተአምር እንደተረፈ ጀልባ : ቁጭ እንዳለ ነበር። በውሃ አለመወሰዱ አስደሰተኝና ልክ ሳላስበው እንደወደቀብኝ ሁሉ ተስገብግቤ በሁለት ጣቶቼ መልሼ አወጣሁት፡፡ ቁልፉን አጥቤ እጄንም ታጠብኩና ወደ መኝታ ቤቴ ተመልሼ አልጋዬ ጫፍ ላይ ቁጭ አልኩ። የምሠራው ግራ ገብቶኝ ዙሪያውን ስቃኝ ቆዬሁ እና እንደገና ተነስቼ በመስኮት ማዬት ጀመርኩ፡፡ ሳያቋርጥ ያቅለሸልሼኛል!! በራቼው ላይ ቆመው መክፈቻ ቁልፍ የጠፋባቼው ሰዎች ስለምን ያዝናሉ? እኔ መክፈቻ ቁልፍ ይዠ በሩ ከነቤቱ፣ ከነባለቤቱ የጠፋብኝ ሰው ነኝ፡፡ ይኼ ቁልፍ ከእንግዲህ የሚከፍተው የትዝታ በሮችን ብቻ ነው። መልሼ ወደዘለበቱ አስገባሁት እና ኮመዲኖው ላይ ወርውሬው ከልጄ ጎን ተኛሁ፤ የኔ ዜማ የሕይወቴ ቁልፍ፡፡ሰላም የሰፈነበት ድንቡሸ ፊቷን እያዬሁ በሐሳብ ነጎድኩ... ብዙ ብዙ አሰብኩ! ለሰዓታት... እናም ለራሴ ምን አልኩ? አይዞኝ አልኩ!
አይዞኝ! አሁን እናት ነኝ፤ ስለ ልጆቸ ዕጣ ፋንታ ማሰብ አለብኝ። ለሞተ ትላንቴ ሳለቃቅስ መኖር ገና የተጀመረ የልጆቼን ነገ ማበላሸት ነው፡፡ እኔ ምርጫዬን ኖሪያለሁ፤ ለዚሀ ውሳኔ ያበቃኝ አስተዳደግም ይሁን ስሜታዊነት ሁሉም ነገር የራሴ ውሳኔ ነበር። በሕይወት ውስጥ ማንኛውንም የውሳኔ ጠጠር _ ከመወርወራችን በፊት፣ ፊት ለፊታችን የቆመ የነገ መስተዋታችን ላይ ምን ሊፈጥር እንደሚችል ማሰብ የእኛው ኃላፊነት ነው፡፡ ግን ደግሞ ሰውነን እና ብዙ ከማስተዋል ጎዳና የሚያስወጣን ስሜት ይኖራል፡፡ _ የእኔው _ ጠጠር _ መስተዋቴን _ ሰንጥቆት ይሆናል እንጂ ጨርሰ አልተንኮታኮተም፡፡ በሕይወት እስካሉ ጨርሶ መንኮታኮት የሚባል ነገር የለም፡፡ ጥሩ ባል ያላት ባለትዳር፣ የአንዲት ቆንጆ ልጅ እናት እና ሁለተኛ ልጅ ያረገዝኩ ሴት ነኝ።ልጆቼ ያልተረበሸ ነገ ያላቼው፣ ማንንም የማይፈሩ፣ ማንንም የማይለማመጡ፤ ሰውን ከመውደድና ከማክበር ያለፈ ዕዳ የሌለባቼው ልጆች እንዲሆኑ የትኛውንም ዋጋ የመክፈል ግዴታ አለብኝ፡፡ አይዞኝ! ጥሩ ወላጅ ማለት ከጊዜ ጎርፍ ፊት ቆሞ መከራና ስቃይን ወደ ትውልድ እንዳያልፍ አግዶ የሚይዝ ጽኑ ግንብ ነው፡፡ አምላኬ ብርታቱን ይስጠኝ። በእርግጥ ባሌን አላፈቅረውም፤ ግን በዚህ የተልከሰከሰ ዘመን ቢያንስ ማግባት የሚባልን ክብር ያጎናጸፈኝ መልካም ሰው ነው፡፡ የእኔ ትላንት ትዳሩን እንዲረብሸው አልፈቅድም፡፡ ብዙዎች ገና ከቤተሰባቼው ጫንቃ በማይወርዱበት ዕድሜ ከሞት ጋር ተናንቆ ለቤተሰቡ አሸናፊነትን ያሳዬ ሰው ነው። ወጣትነቱን ሰውቶ፣ በስደት ተንከራቶ ያቆመው ሕይወት ነው፡፡ ቢያንስ የባልነት መብቱን ማክበር የልጆቼን ግማሸ ማንነት ማክበር ነው፡፡ ውስጣችን በፍቅር ካልተገዛ ቢያንስ ለሞራል ሕግ እንዲገዛ ማስገደድ አለብን፡፡ ሕመም ቢኖረው እንኳን ላፈቀሩን፣ ባያፈቅሩንም ላከበሩን የሚከፈል ትንሽ ዋጋ ነው፡፡
ምርጫዋን ተከትላ መንጎዷ ምን ዓይነት ጥንካሬ ቢኖራት ነው!?...ከሌላ ሰው ልጅ ወልዳለች ተብሏል፤ ምናይነት እናት ነው የምትሆነው? አባባን አታፍቅረው እሺ እኔም ባሌን አላፈቅረውም፣ ሌላ የምታፈቅረው ሰው ይኑር እኔም ሌላ ሰው ልቤ ውስጥ አለ ግን ከማላፈቅረው ሰው ብወልዳትም ልጄን ትቼ ከምሄድ ሞቴን እመርጣለሁ! እንዴት ያንን ቻለች? ዕድሜ ልኳን የልጆቿ ናፍቆት ቅጣት እንደሚሆንባት አልጠራጠርም፤ ግን ደግሞ ከማያፈቅሩት ጋር መኖርም ቅጣት ነው። የትኛውም ምቾት የትኛውም ክብርና እንክብካቤ የማይፈውሰው ባርነት፣ መሰሪያ የታጠቀ ወታደር በሩ ላይ ባይቆምም፣ ከፍቅር ውጭ በማንኛውም ሰበብ የተጣመሩበት ትዳር እስር ቤት ነው፤ መስኮት የእስረኛ ነፍስ መነፅር ሳይሆን ይቀራል? በቆምኩበት ቡና ይሼተኛል እናም ያቅለሸልሼኛል አውቀዋለሁ ስሜቱን ሁለተኛ አርግዣለሁ፡፡ ምንም የተለዬ ስሜት አልተሰማኝም፡፡ እንዲሁ ትውልድ የሚባል ነገር በውስጤ የሚያልፍብኝ ባዶ መተላለፊያ ነገር ከመሆን ስሜት ውጭ! ተመልሼ አልጋዬ ጫፍ ላይ ተቀመጥኩና ካለምንም ምክንያት ኮሜዲኖው ላይ የተቀመጡትን ቁልፎች አነሳሁ፡፡ ወደ አምስት የሚሆኑ በቁልፍ መያዣ ዘለበት የተሰኩ ቁልፎች ናቸው፤ የመኪና ቁልፍ የቤት ቁልፍ የካዝና ቁልፍ(እዚያ ካዝና ውስጥ ቁጥር ስፍር የሌላቼው የወርቅ ጌጣጌጦች(የዚህ የባሌ ስጦታ) እና የጋብቻ ዶክሜንቶች አሉ፡፡ ከእኔ በስተቀር ማንም የምን ቁልፍ እንደሆነ የማያውቀው አንድ መካከለኛ ቁልፍ የማንጠለጥላቼው ጥቂት ቁልፎች ጋር ሁሌም አለ። ለዓመታት አንጠልጥዬው ስዞር ማንም(ያው ማንም ባለቤቴ ነው) የምንድን ቁልፍ ነው? ብሎኝ አያውቅም። ጠባሳችን የት ላይ እንዳለ ከራሳችን በስተቀር ማን ያውቃል?! አብርሃም የሰጠኝ የቤቱ ቁልፍ ነበር። ምንም ነገር የለኝም፤ ፎቶው የለኝም፣ ሰጥቶኝ የሚያውቀው ስጦታ የለም፣ ከእርሱ የቀረኝ ብቼኛ ነገር የቤቱ ቁልፍ ነበር፡፡ ይኼ በእጄ ስይዘው እንደ አንዳች ነገር ሰላም የሚሰጠኝ ቁልፍ፤ ስንት ቀን ይኼን ቁልፍ በእጆቼ እያገላበጥኩ እንደ ተአምር አዬሁት? ስንቴ በሃሳብ ነጎድኩ!? ያንን የኮንዶሚኒዬም
የብረት በር ስከፍት ልቤ በደስታ ተመንጥቃ ልትወጣ ትደርስ ነበር። ከቀለበት እኩል የሆነ ቃልኪዳን ነገር ያለበት ቁልፍ ይመስለኛል፡፡ ባወጣ ባወርድ አልገለጥልሽ ያለኝ አንድ ነገር፣ አንዳንዴ ምክንያቱን ለራሳችን እንኳ በማይገባን ምክንያት ለቅርቦቻችን፣ ብዙ ለዋሉልን- ባይውሉልንም፣ ምንም ላልበደሉን ሰዎች ይሁዳ ሆነን አሳልፈን ለሐዘን ስንሰጣቼው፤ ሕይወታችንን ለመሳቀሉ ክፉዎች ግን፣ እንደ ክርስቶስ ካልተሰቀልንላችሁ ስንል የመገኜታችን ነገር ምን ይሆን ሚስጥሩ? ብስጭት ውስጤን ሞላው፤ ቁልፎቹ የተሰኩበትን ዘለበት ፈልቅቄ ያንን ቁልፍ ነጥዬ አወጣሁትና በብስጭት ወደ መፀዳጃ ቤት ገብቼ የሽንት ቤቱ መቀመጫ ውስጥ ወረወርኩት፡፡ ሸክላው ላይ ተቅጨልጭሎ ውሃው ውስጥ በእርጋታ ገብቶ ቁጭ አለ፤ የውሃ መልቀቂያውን ባለ በሌለ ኃይሌ ስጫነው ንጹህ ውሃ እየተዥጎደጎደ ቁልቁል ጎርፎ ሲያልቅ ቁልፉ ከመዓበል በተአምር እንደተረፈ ጀልባ : ቁጭ እንዳለ ነበር። በውሃ አለመወሰዱ አስደሰተኝና ልክ ሳላስበው እንደወደቀብኝ ሁሉ ተስገብግቤ በሁለት ጣቶቼ መልሼ አወጣሁት፡፡ ቁልፉን አጥቤ እጄንም ታጠብኩና ወደ መኝታ ቤቴ ተመልሼ አልጋዬ ጫፍ ላይ ቁጭ አልኩ። የምሠራው ግራ ገብቶኝ ዙሪያውን ስቃኝ ቆዬሁ እና እንደገና ተነስቼ በመስኮት ማዬት ጀመርኩ፡፡ ሳያቋርጥ ያቅለሸልሼኛል!! በራቼው ላይ ቆመው መክፈቻ ቁልፍ የጠፋባቼው ሰዎች ስለምን ያዝናሉ? እኔ መክፈቻ ቁልፍ ይዠ በሩ ከነቤቱ፣ ከነባለቤቱ የጠፋብኝ ሰው ነኝ፡፡ ይኼ ቁልፍ ከእንግዲህ የሚከፍተው የትዝታ በሮችን ብቻ ነው። መልሼ ወደዘለበቱ አስገባሁት እና ኮመዲኖው ላይ ወርውሬው ከልጄ ጎን ተኛሁ፤ የኔ ዜማ የሕይወቴ ቁልፍ፡፡ሰላም የሰፈነበት ድንቡሸ ፊቷን እያዬሁ በሐሳብ ነጎድኩ... ብዙ ብዙ አሰብኩ! ለሰዓታት... እናም ለራሴ ምን አልኩ? አይዞኝ አልኩ!
አይዞኝ! አሁን እናት ነኝ፤ ስለ ልጆቸ ዕጣ ፋንታ ማሰብ አለብኝ። ለሞተ ትላንቴ ሳለቃቅስ መኖር ገና የተጀመረ የልጆቼን ነገ ማበላሸት ነው፡፡ እኔ ምርጫዬን ኖሪያለሁ፤ ለዚሀ ውሳኔ ያበቃኝ አስተዳደግም ይሁን ስሜታዊነት ሁሉም ነገር የራሴ ውሳኔ ነበር። በሕይወት ውስጥ ማንኛውንም የውሳኔ ጠጠር _ ከመወርወራችን በፊት፣ ፊት ለፊታችን የቆመ የነገ መስተዋታችን ላይ ምን ሊፈጥር እንደሚችል ማሰብ የእኛው ኃላፊነት ነው፡፡ ግን ደግሞ ሰውነን እና ብዙ ከማስተዋል ጎዳና የሚያስወጣን ስሜት ይኖራል፡፡ _ የእኔው _ ጠጠር _ መስተዋቴን _ ሰንጥቆት ይሆናል እንጂ ጨርሰ አልተንኮታኮተም፡፡ በሕይወት እስካሉ ጨርሶ መንኮታኮት የሚባል ነገር የለም፡፡ ጥሩ ባል ያላት ባለትዳር፣ የአንዲት ቆንጆ ልጅ እናት እና ሁለተኛ ልጅ ያረገዝኩ ሴት ነኝ።ልጆቼ ያልተረበሸ ነገ ያላቼው፣ ማንንም የማይፈሩ፣ ማንንም የማይለማመጡ፤ ሰውን ከመውደድና ከማክበር ያለፈ ዕዳ የሌለባቼው ልጆች እንዲሆኑ የትኛውንም ዋጋ የመክፈል ግዴታ አለብኝ፡፡ አይዞኝ! ጥሩ ወላጅ ማለት ከጊዜ ጎርፍ ፊት ቆሞ መከራና ስቃይን ወደ ትውልድ እንዳያልፍ አግዶ የሚይዝ ጽኑ ግንብ ነው፡፡ አምላኬ ብርታቱን ይስጠኝ። በእርግጥ ባሌን አላፈቅረውም፤ ግን በዚህ የተልከሰከሰ ዘመን ቢያንስ ማግባት የሚባልን ክብር ያጎናጸፈኝ መልካም ሰው ነው፡፡ የእኔ ትላንት ትዳሩን እንዲረብሸው አልፈቅድም፡፡ ብዙዎች ገና ከቤተሰባቼው ጫንቃ በማይወርዱበት ዕድሜ ከሞት ጋር ተናንቆ ለቤተሰቡ አሸናፊነትን ያሳዬ ሰው ነው። ወጣትነቱን ሰውቶ፣ በስደት ተንከራቶ ያቆመው ሕይወት ነው፡፡ ቢያንስ የባልነት መብቱን ማክበር የልጆቼን ግማሸ ማንነት ማክበር ነው፡፡ ውስጣችን በፍቅር ካልተገዛ ቢያንስ ለሞራል ሕግ እንዲገዛ ማስገደድ አለብን፡፡ ሕመም ቢኖረው እንኳን ላፈቀሩን፣ ባያፈቅሩንም ላከበሩን የሚከፈል ትንሽ ዋጋ ነው፡፡
👍35❤8
ደግሞስ ነገን ማን ያውቃል? ፍቅር ራሳችንን በሰጠነው ቁና ልክ ይሰፈር እንደሆነ ምን ይታወቃል? ዓይነቱ ይለያይ እንደሆን እንጂ ሕይወት እስካለ፣ ማፍቀር ይኖራል፡፡ ልብሳችንን ጥለን _ ከደመና በላይ ባንሳንፈፍም፣ ማንም ሰው በጎጆው ጠሪያ ሥር ትንሽ ፍቅር _ አያጣም፡፡ _ ራስንም _ ቤተሰብንም ጤና ከመንሳት መተሳሰብንና የጋራ ኃላፊነትን ፍቅር ነው ብሎ ማመን ሳይሻል አይቀርም፡፡ ትዳር ከፀሐይ ቢከልለንም በየቤታችን ጭል ጭል በምትል ኩራዝም ቢሆን ከብርሃን ጨርሰን አንቆራረጥም፤ አይዞኝ! ዓይኖቼን ከድኜ እንዲህ ሳስብ፣ የመኝታ ቤቱ በር በቀስታ ሲከፈት ሰማሁ፤ ከአከፋፈቱ ባለቤቴ እንደሆነ አውቂያለሁ። ትንሽ ጸጥታ ሰፈነ፤ አንገቱን ብቅ አድርጎ እኔና ዜማን በርህራሄ እና በፍቅር እያዬን እንደሆነ አውቃለሁ። በቀስታ ተራምዶ የልብስ ማስቀመጫውን ሲከፍት እና
ሲዘጋ እሰማለሁ። ወደ ተኛንበት መጥቶ የምወዳትን ለስላሳ ብርድ ልብስ ደረበልን እና ግንባሬን በስሱ ስሞኝ እንደ አገባቡ በቀስታ ወጥቶ ሲሄድ ዕንባዬ ተዘረገፈ።
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
ሲዘጋ እሰማለሁ። ወደ ተኛንበት መጥቶ የምወዳትን ለስላሳ ብርድ ልብስ ደረበልን እና ግንባሬን በስሱ ስሞኝ እንደ አገባቡ በቀስታ ወጥቶ ሲሄድ ዕንባዬ ተዘረገፈ።
ይቀጥላል...
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
👍31❤3
''አስጠላኸኝ'' አለችው
''ለምን'' አላላትም
:
ያውቃታል ጠንቅቆ ምክንያት የላትም።
ካቻምና እንደሆነው :
እርሱ ጋር ስትመጣ
የበፊት ጌታዋን
''አስጠላኝ'' ብላ ነው።
አንዳንዱ ለመሄድ
ሰበብ ስለሌለው
ፍቅርህን ለመግደል
:
ሲፈልግ ይውላል
ያንተን አንድ በደል!
ለምን ብለኽ አንጀትህን አታላውሰው
:
አቋቋሙ ያስታውቃል
እንደሚሄድ አንዳንድ ሰው።
🎴ኤልያስ ሽታኹን🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
''ለምን'' አላላትም
:
ያውቃታል ጠንቅቆ ምክንያት የላትም።
ካቻምና እንደሆነው :
እርሱ ጋር ስትመጣ
የበፊት ጌታዋን
''አስጠላኝ'' ብላ ነው።
አንዳንዱ ለመሄድ
ሰበብ ስለሌለው
ፍቅርህን ለመግደል
:
ሲፈልግ ይውላል
ያንተን አንድ በደል!
ለምን ብለኽ አንጀትህን አታላውሰው
:
አቋቋሙ ያስታውቃል
እንደሚሄድ አንዳንድ ሰው።
🎴ኤልያስ ሽታኹን🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍38❤6🥰4
#አበጁ!
...
አዳምና ሄዋን፣ ከገነት ባይወጡ፣
ያቺን ዕፀ-በለስ፣ ፍሬዋን ባይውጡ፣
አይጥመኝም ነበር፣ ሕይወት እንዳሁኑ፣
ሳይሠሩ መቀለብ፣ መኖር ሳይቦዝኑ፡፡
እንኳን ተሳሳቱ፣ እኔስ ደስ ብሎኛል፣
ሳይሠራ ‘ሚበላ፣ ወትሮም ያቆስለኛል፡፡🤔
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
...
አዳምና ሄዋን፣ ከገነት ባይወጡ፣
ያቺን ዕፀ-በለስ፣ ፍሬዋን ባይውጡ፣
አይጥመኝም ነበር፣ ሕይወት እንዳሁኑ፣
ሳይሠሩ መቀለብ፣ መኖር ሳይቦዝኑ፡፡
እንኳን ተሳሳቱ፣ እኔስ ደስ ብሎኛል፣
ሳይሠራ ‘ሚበላ፣ ወትሮም ያቆስለኛል፡፡🤔
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍15
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሰሎሞን ድቅቅ ካደረገው እንቅልፍ ቢነቃም
ዓይኖቹ አልገለጥ ስላሉት አሻሽቶ ሊያነቃቸው
ፈልጐ ቀኝ እጁን ለማንቀሳቀስ ሲሞክር
አልተቻለውም፤የሆነ እጁ ላይ የተጫነ ነገር አለ፤የሆነ ሰው አቅፎል..‹‹ወይ እዳዬ !!ማታ ተሳሳትኩ መሰለኝ... ሴት ይዤ ገብቼያለሁ ማለት ነው፡፡›› ሲል አሰበ፤ እሱን ተወውና
ግራውን ሞከረ ተመሳሳይ ነው፡፡በዚህን ጊዜ ደነገጠ ..እንዴት ሁለት ሴት ልገዛ እችላለው?›› ድንጋጤው አይኖቹ ተበርግደው እንዲከፈቱ አገዘው ፡፡ወደ ቀኙ ዞረና አየ…..ልጁ ዕፀ-ህይወት ናት ዝርግትግት ብላ ክንዱን
ተንተርሳ በነጻነት ተኝታለች...ወደ ግራው
ዞረ..ሌለኛዋ ልጁ ዕፀ‐ፍቅር በተመሳሳይ ሁኔታ ግራ ክንዱ ላይ ተመቻችታ ተኝታለች፡፡ከእሷ ቀጥሎ ቢጃማ ለባሽ የሆነች ገዘፍ ያለች ሴት ከአንሶላው ሳትወጣ ቁጭ ብላ መፅሀፍ
እያነበበች ነው፡፡
‹‹የፈጣሪ ያለህ!!››አለ የልጆቹ ሲገርመው ከአመታት በፊት የፈታት ሚስቱን ከጎኑ ሲመለከት፡፡ ‹‹ምን ልትሰራ እሱ ቤርጓ ተገኘች?..የቤቱን ዙሪያ ገባ በግርምት ቃኘ... ቤርጎው አይደለም ያለው ፤ የድሮ ቤቱ... የበፊት መኝታው ክፍሉ ውስጥ..የበፊት አልጋው ላይ ከበፊት ሚስቱ ጋር…የሚገርም ጉዳይ ነው፡፡
‹‹እየቃዠው መሆን አለበት?››ድምፅ አውጥቶ ተናገረ፡፡
የውብዳር የተናገረውን በትክክል አጥርታ ባትሰማም የሆነ ነገር እንዳለ ድምፁ ጆሮዋ ጋር ስለደረሰ የምታነበውን መጽሀፍ ቅዱስ በመክደን ያቀረቀረ ግንባሯን ወደ ላይ ቀና አደረገችና << ነቃህ እንዴ….?እንዴት ነው ሰላም አደርክ?››አለችው በፍጹም ትህትና ፡፡
ለእሷ ጥያቄ መልስ ከመስጠት ይልቅ የራሱን ጥያቄ አስቀደመ ‹‹የት ነው ያለሁት?››ጠየቃት፡፡
‹‹ቤትህ ነዋ፡፡››
እንደመበርገግ አለና ልጆቹን ከክንዶቹ ላይ አንሻራቶ እራሱን ነጻ በማድረግ ከእሷ ጋር በተመሳሳይ ሁኔታ ተቀመጠ፡፡
‹‹ቀስ... ቀስ.. ልጆቸህን ትቀሰቅሳቸዋለህ››አለችው በለሆሳሳ፡፡
‹‹ቆይ ማታ ሰክሬ ነው አይደል የመጣሁት .. ? በጣም እረበሽኳችሁ እንዴ....? ስትረብሽ ልጆችህም አይተውህ ነበር እንዳትይኝ ብቻ… አዝናለሁ፡፡ እንዲህ ለማድረግ ፈልጌ አልነበረም፡፡ ትንሽ ተበሳጭቼ ስለነበር በዛ ላይ መጠጥ አብዝቼ ስወስድበት እራሴን አስቶኝ ነበር ማለት ነው..አንቺም እኮ ትክክል አይደለሽም፤ስመጣ ዝም ብለሽ ታስገቢኛለሽ እንዴ…? ገና ከውጭ በራፍን አልፌ ሳልገባ ዘበኛው እንዲመልሰኝ አታደርጊም ነበር?››
ዝም ብላ በፍዘት ስታዳምጠው ከቆየች በኃላ << ማታ ስለሆነው ሁሉ ምንም ነገር አታስታውስም ማለት ነው?›.አለችው፤ የሆነ ሀይለኛ የሚቀስፍ ስጋት እና የሚቀዘቅዝ ፍርሀት በሰውነቷ እየተሰራጨባት፡፡
‹‹ቆይ ቆይ..ማታ እኔ ቤርጎ አንቺ…››የሆነ እንደህልም አይነት ትዝታ በአዕምሮዎ ብልጭ ድርግም አለበት፡፡
‹‹አዎ መጥቼ ነበር፡፡››
‹‹አዎ እንደ እሱ በይኝ.. እንጂማ ያን ያህል ላብድ አልችልም፡፡ >>
‹‹የምን እብደት አመጣህብኝ?››
‹‹...ቀጥታ ዝም ብዬ እዚህ በመምጣት ካላደርኩ አልልማ ... አንቺን እዛ ሳይ ተከትዬሽ መጥቼ እንጂ..፡››
‹‹እንደዛም አይደለም፡፡››
‹‹ታዲያ እንዴት ነው?››
‹‹እኔ ነኝ ለምኜህ ማለት ይቅርታ ጠይቄህ ይዤህ የመጣሁት...››
‹‹እየቀለድሽ አይደለም አይደል?››
‹‹እውነቴን ነው ሶል... ተነጋግረን ተስማምተን ነበር የመጣሀው፡፡ጥፋት ያጠፋህ መስሎ ከተሰማህ እንኳን ጥፋቱ የእኔ ነው እንጂ ያአንተ አይደለም፡፡ አንተ ምንም አላደረግክም …እኔም ግን ወድጄ አይደለም ፤ እስቲ ልጆቻችንን እያቸው፤ዛሬ ከጎናቸው ብትሆን እንዴት የሰላም እንቅልፍ እንደተኙ.. አቤት ማታ ቀስቅሰህ መጥቼያለሁ ስትላቸው የተደሰቱት መደሰት ልነግርህ አልችልም..ታዲያ ለእነሱ ስትል ይቅር ብትለኝ ምን አለበት..?በቃ ምንም ልበድልህ ... ምንም ላጥፋ ለእነሱ ስትል ልትረሳልኝ አትችልም?››
‹‹ኧረ ቆይ.. አንቺ ባጠፋሽው መጠን እኮ እኔም አጥፍቼያለሁ›..
‹‹ታዲያ በቃ ይቅር እንባባላ..በቃ በስካር
መንፈስም ቢሆን ወደ ቤትህ አንዴ ገብተሀል
..በፈጠረህ በዚህ በምታምንበት መጽሀፍ
ቅዱስ ልለምንህ ፤ ተመልሰህ ከቤትህ
አትውጣ... ከልጆችህ ጋር ኑር...አንተ
ከምትወጣ እኔ ብወጣ ይሻለኛል...ሴት ልጆች
አባታቸውን አብልጠው ይወዳሉ ሲባል አባባል
ብቻ ይመስለኝ ነበር..በራሴ ልጆች ነው እውነት
መሆኑን ያረጋገጥኩት... አንተን አጥተው መኖር
በጣም ነው የሚከብዳቸው... ስለዚህ
ባክህ..ባክህ››በማለት በቃላትም ...በአይኖቿ
እርግብግብታም ተለማመጠችው፡፡እጁን ላካና አቅፎ ወደ ራሱ በመጎተት ደረቱ ላይ ለጥፎት በጆሮዋ ‹‹እኔም የትም አልሄድ ..አንቺ
እንዳልሽው በቃ ያለፈውን እንርሳው... የውሾን
ነገር ያነሳ ውሾ ይሁን››አላት፡፡
‹‹እሺ የእኔ ጌታ አመሰግናለሁ››አለችውና የሚንጠባጠበውን እንባዋን በቀኝ እጇ እያበሰች ከእቅፉ ወጥታ አልጋውን ለቃ ወረደች፡፡በዚህ ጊዜ በመሀከላቸው ያለችው ዕፀ- ህይወት ከእንቅልፏ ባና ዓይኖቿን ከመግለጧ በፊት መጀመሪያ የጠየቀችው ጥያቄ‹‹አባቴስ?›› የሚል ነበር፡፡
‹‹አለሁልሽ የእኔ ቆንጆ >> ብሎ ወደ ራሱ አስጠግቶ አቀፋት... ሙሉ በሙሉ ነቃችና እላዩ ላይ ተንጠልጥላ እያገላበጠች ትስመው ጀመር፡፡ በዚህም አረካችም መንታ እህቷንም ቀሰቀሰቻት ..ሰሎሞን ተይ ትተኛ ቢላትም ልታዳምጠው አልፈለገችም፡፡ ሁለቱም ልጆቹ ለመጀመሪያ ቀን ያዩት ይመስል ትንፋሽ እስኪያጥረው እና ድክም እሲኪለው ተላፉት ፣ሳሙት፣እላዩ ላይ ጨፈሩ፡፡ በመጨረሻ የውብዳር ነበረች በግድ አላቃ ለቁርስ መኝታ ቤቱን ለቀው ወደ ምግብ መመገቢያ ቤት እንዲሄዱ ያስገደቻቸው፡፡
በፊት አብሯቸው ይኖር በነበረበት በመጀመሪያዎቹ የፍቅር ዓመታት በእጇ ትሰራለት የነበረውን እና እሱም በጣም እየወደደውና እሷንም እያመሰገነው ይበላው የነበረውን ምግብ ነበር ሰርታ ለቁርስ ያቀረበችው ፡፡በሳቅ እና በጨወታ ታጅበው
ቁርሳቸውን እየበሉ ግማሽ እንደደረሱ የሳሎኑ በራፍ ተንኳኳ፡፡
‹‹ይግቡ ..ክፍት ነው›› አለች የውብዳር ከመቀመጫዋ ሳትነሳ.፡
በራፉ ተከፈተ..ሁሴን ነበረ የመጣው ፡፡
‹‹እየተጣራጠርኩ ነው የመጣሁት ስልክሽ አይሰ......››ንግግሩን አቋረጠ፡፡እርምጃውንም መሀል ሳሎን ላይ ገታው፡፡የሰሎሞን እዛ ቤት ውስጥ መገኘት ፍጽም ከግምቱ ውጭ የሆነ ክስተት ነበር... የሆነ ውሽማው ቤት ሊሰርቅ የሄደ ሰው ከባልዬው ጋር የመፋጠጥ አጋጣሚ እንዳጋጠመው ሰው ነው አደነጋገጡ፡፡
<< ና እንጂ ....አንተ እንወድሀለን ማለት ነው .. ቁርስ ላይ ደረስክ.…‹ሲበሉ አድርሰኝ ሲጣሉ መልሰኝ› የሚባለው እንደዚህ ነው››አለችው የውብዳር፡፡
ሁሴን ግን የእሷን ወሬ አልሰማም‹‹ይሄ ሰውዬ
እዚህ ምን ይሰራል? ››አላት እንደምንም እግሮቹን አነቃንቆ ወደ እነሱ እየተጠጋ።
‹‹እቤቱ ከልጆቹ እና ከሚስቱ ጋር ቁጭ ብሎ ቁርስ እየበላ ነዋ››
‹‹..ከልጆቹ እና ከሚስቱ ጋር >> ልትል አስባ ነበር ያልተረጋገጠውን የሚስትነት ማዕረጓን መልሳ የዋጠችው›› የምታድርበት ሆቴል እኮ ሁለቴ ነዋ የመጣሁት ስልክህም ዝግ ነው ..ግራ ሲገባኝ ጊዜዬን ከማባክን እነዚህ ልጆች ልይ ብዬ ወደ እዚህ ጎራ ማለቴ እኮ ነበር..እንጂማ.. ››በማለት ለልጆች ይዞላቸው የመጣውን ቸኮሌት አከፋፈሏቸው ወንበር ስቦ ተቀመጠ ፤አመስግነው ተቀበሉት፡፡
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሶስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሰሎሞን ድቅቅ ካደረገው እንቅልፍ ቢነቃም
ዓይኖቹ አልገለጥ ስላሉት አሻሽቶ ሊያነቃቸው
ፈልጐ ቀኝ እጁን ለማንቀሳቀስ ሲሞክር
አልተቻለውም፤የሆነ እጁ ላይ የተጫነ ነገር አለ፤የሆነ ሰው አቅፎል..‹‹ወይ እዳዬ !!ማታ ተሳሳትኩ መሰለኝ... ሴት ይዤ ገብቼያለሁ ማለት ነው፡፡›› ሲል አሰበ፤ እሱን ተወውና
ግራውን ሞከረ ተመሳሳይ ነው፡፡በዚህን ጊዜ ደነገጠ ..እንዴት ሁለት ሴት ልገዛ እችላለው?›› ድንጋጤው አይኖቹ ተበርግደው እንዲከፈቱ አገዘው ፡፡ወደ ቀኙ ዞረና አየ…..ልጁ ዕፀ-ህይወት ናት ዝርግትግት ብላ ክንዱን
ተንተርሳ በነጻነት ተኝታለች...ወደ ግራው
ዞረ..ሌለኛዋ ልጁ ዕፀ‐ፍቅር በተመሳሳይ ሁኔታ ግራ ክንዱ ላይ ተመቻችታ ተኝታለች፡፡ከእሷ ቀጥሎ ቢጃማ ለባሽ የሆነች ገዘፍ ያለች ሴት ከአንሶላው ሳትወጣ ቁጭ ብላ መፅሀፍ
እያነበበች ነው፡፡
‹‹የፈጣሪ ያለህ!!››አለ የልጆቹ ሲገርመው ከአመታት በፊት የፈታት ሚስቱን ከጎኑ ሲመለከት፡፡ ‹‹ምን ልትሰራ እሱ ቤርጓ ተገኘች?..የቤቱን ዙሪያ ገባ በግርምት ቃኘ... ቤርጎው አይደለም ያለው ፤ የድሮ ቤቱ... የበፊት መኝታው ክፍሉ ውስጥ..የበፊት አልጋው ላይ ከበፊት ሚስቱ ጋር…የሚገርም ጉዳይ ነው፡፡
‹‹እየቃዠው መሆን አለበት?››ድምፅ አውጥቶ ተናገረ፡፡
የውብዳር የተናገረውን በትክክል አጥርታ ባትሰማም የሆነ ነገር እንዳለ ድምፁ ጆሮዋ ጋር ስለደረሰ የምታነበውን መጽሀፍ ቅዱስ በመክደን ያቀረቀረ ግንባሯን ወደ ላይ ቀና አደረገችና << ነቃህ እንዴ….?እንዴት ነው ሰላም አደርክ?››አለችው በፍጹም ትህትና ፡፡
ለእሷ ጥያቄ መልስ ከመስጠት ይልቅ የራሱን ጥያቄ አስቀደመ ‹‹የት ነው ያለሁት?››ጠየቃት፡፡
‹‹ቤትህ ነዋ፡፡››
እንደመበርገግ አለና ልጆቹን ከክንዶቹ ላይ አንሻራቶ እራሱን ነጻ በማድረግ ከእሷ ጋር በተመሳሳይ ሁኔታ ተቀመጠ፡፡
‹‹ቀስ... ቀስ.. ልጆቸህን ትቀሰቅሳቸዋለህ››አለችው በለሆሳሳ፡፡
‹‹ቆይ ማታ ሰክሬ ነው አይደል የመጣሁት .. ? በጣም እረበሽኳችሁ እንዴ....? ስትረብሽ ልጆችህም አይተውህ ነበር እንዳትይኝ ብቻ… አዝናለሁ፡፡ እንዲህ ለማድረግ ፈልጌ አልነበረም፡፡ ትንሽ ተበሳጭቼ ስለነበር በዛ ላይ መጠጥ አብዝቼ ስወስድበት እራሴን አስቶኝ ነበር ማለት ነው..አንቺም እኮ ትክክል አይደለሽም፤ስመጣ ዝም ብለሽ ታስገቢኛለሽ እንዴ…? ገና ከውጭ በራፍን አልፌ ሳልገባ ዘበኛው እንዲመልሰኝ አታደርጊም ነበር?››
ዝም ብላ በፍዘት ስታዳምጠው ከቆየች በኃላ << ማታ ስለሆነው ሁሉ ምንም ነገር አታስታውስም ማለት ነው?›.አለችው፤ የሆነ ሀይለኛ የሚቀስፍ ስጋት እና የሚቀዘቅዝ ፍርሀት በሰውነቷ እየተሰራጨባት፡፡
‹‹ቆይ ቆይ..ማታ እኔ ቤርጎ አንቺ…››የሆነ እንደህልም አይነት ትዝታ በአዕምሮዎ ብልጭ ድርግም አለበት፡፡
‹‹አዎ መጥቼ ነበር፡፡››
‹‹አዎ እንደ እሱ በይኝ.. እንጂማ ያን ያህል ላብድ አልችልም፡፡ >>
‹‹የምን እብደት አመጣህብኝ?››
‹‹...ቀጥታ ዝም ብዬ እዚህ በመምጣት ካላደርኩ አልልማ ... አንቺን እዛ ሳይ ተከትዬሽ መጥቼ እንጂ..፡››
‹‹እንደዛም አይደለም፡፡››
‹‹ታዲያ እንዴት ነው?››
‹‹እኔ ነኝ ለምኜህ ማለት ይቅርታ ጠይቄህ ይዤህ የመጣሁት...››
‹‹እየቀለድሽ አይደለም አይደል?››
‹‹እውነቴን ነው ሶል... ተነጋግረን ተስማምተን ነበር የመጣሀው፡፡ጥፋት ያጠፋህ መስሎ ከተሰማህ እንኳን ጥፋቱ የእኔ ነው እንጂ ያአንተ አይደለም፡፡ አንተ ምንም አላደረግክም …እኔም ግን ወድጄ አይደለም ፤ እስቲ ልጆቻችንን እያቸው፤ዛሬ ከጎናቸው ብትሆን እንዴት የሰላም እንቅልፍ እንደተኙ.. አቤት ማታ ቀስቅሰህ መጥቼያለሁ ስትላቸው የተደሰቱት መደሰት ልነግርህ አልችልም..ታዲያ ለእነሱ ስትል ይቅር ብትለኝ ምን አለበት..?በቃ ምንም ልበድልህ ... ምንም ላጥፋ ለእነሱ ስትል ልትረሳልኝ አትችልም?››
‹‹ኧረ ቆይ.. አንቺ ባጠፋሽው መጠን እኮ እኔም አጥፍቼያለሁ›..
‹‹ታዲያ በቃ ይቅር እንባባላ..በቃ በስካር
መንፈስም ቢሆን ወደ ቤትህ አንዴ ገብተሀል
..በፈጠረህ በዚህ በምታምንበት መጽሀፍ
ቅዱስ ልለምንህ ፤ ተመልሰህ ከቤትህ
አትውጣ... ከልጆችህ ጋር ኑር...አንተ
ከምትወጣ እኔ ብወጣ ይሻለኛል...ሴት ልጆች
አባታቸውን አብልጠው ይወዳሉ ሲባል አባባል
ብቻ ይመስለኝ ነበር..በራሴ ልጆች ነው እውነት
መሆኑን ያረጋገጥኩት... አንተን አጥተው መኖር
በጣም ነው የሚከብዳቸው... ስለዚህ
ባክህ..ባክህ››በማለት በቃላትም ...በአይኖቿ
እርግብግብታም ተለማመጠችው፡፡እጁን ላካና አቅፎ ወደ ራሱ በመጎተት ደረቱ ላይ ለጥፎት በጆሮዋ ‹‹እኔም የትም አልሄድ ..አንቺ
እንዳልሽው በቃ ያለፈውን እንርሳው... የውሾን
ነገር ያነሳ ውሾ ይሁን››አላት፡፡
‹‹እሺ የእኔ ጌታ አመሰግናለሁ››አለችውና የሚንጠባጠበውን እንባዋን በቀኝ እጇ እያበሰች ከእቅፉ ወጥታ አልጋውን ለቃ ወረደች፡፡በዚህ ጊዜ በመሀከላቸው ያለችው ዕፀ- ህይወት ከእንቅልፏ ባና ዓይኖቿን ከመግለጧ በፊት መጀመሪያ የጠየቀችው ጥያቄ‹‹አባቴስ?›› የሚል ነበር፡፡
‹‹አለሁልሽ የእኔ ቆንጆ >> ብሎ ወደ ራሱ አስጠግቶ አቀፋት... ሙሉ በሙሉ ነቃችና እላዩ ላይ ተንጠልጥላ እያገላበጠች ትስመው ጀመር፡፡ በዚህም አረካችም መንታ እህቷንም ቀሰቀሰቻት ..ሰሎሞን ተይ ትተኛ ቢላትም ልታዳምጠው አልፈለገችም፡፡ ሁለቱም ልጆቹ ለመጀመሪያ ቀን ያዩት ይመስል ትንፋሽ እስኪያጥረው እና ድክም እሲኪለው ተላፉት ፣ሳሙት፣እላዩ ላይ ጨፈሩ፡፡ በመጨረሻ የውብዳር ነበረች በግድ አላቃ ለቁርስ መኝታ ቤቱን ለቀው ወደ ምግብ መመገቢያ ቤት እንዲሄዱ ያስገደቻቸው፡፡
በፊት አብሯቸው ይኖር በነበረበት በመጀመሪያዎቹ የፍቅር ዓመታት በእጇ ትሰራለት የነበረውን እና እሱም በጣም እየወደደውና እሷንም እያመሰገነው ይበላው የነበረውን ምግብ ነበር ሰርታ ለቁርስ ያቀረበችው ፡፡በሳቅ እና በጨወታ ታጅበው
ቁርሳቸውን እየበሉ ግማሽ እንደደረሱ የሳሎኑ በራፍ ተንኳኳ፡፡
‹‹ይግቡ ..ክፍት ነው›› አለች የውብዳር ከመቀመጫዋ ሳትነሳ.፡
በራፉ ተከፈተ..ሁሴን ነበረ የመጣው ፡፡
‹‹እየተጣራጠርኩ ነው የመጣሁት ስልክሽ አይሰ......››ንግግሩን አቋረጠ፡፡እርምጃውንም መሀል ሳሎን ላይ ገታው፡፡የሰሎሞን እዛ ቤት ውስጥ መገኘት ፍጽም ከግምቱ ውጭ የሆነ ክስተት ነበር... የሆነ ውሽማው ቤት ሊሰርቅ የሄደ ሰው ከባልዬው ጋር የመፋጠጥ አጋጣሚ እንዳጋጠመው ሰው ነው አደነጋገጡ፡፡
<< ና እንጂ ....አንተ እንወድሀለን ማለት ነው .. ቁርስ ላይ ደረስክ.…‹ሲበሉ አድርሰኝ ሲጣሉ መልሰኝ› የሚባለው እንደዚህ ነው››አለችው የውብዳር፡፡
ሁሴን ግን የእሷን ወሬ አልሰማም‹‹ይሄ ሰውዬ
እዚህ ምን ይሰራል? ››አላት እንደምንም እግሮቹን አነቃንቆ ወደ እነሱ እየተጠጋ።
‹‹እቤቱ ከልጆቹ እና ከሚስቱ ጋር ቁጭ ብሎ ቁርስ እየበላ ነዋ››
‹‹..ከልጆቹ እና ከሚስቱ ጋር >> ልትል አስባ ነበር ያልተረጋገጠውን የሚስትነት ማዕረጓን መልሳ የዋጠችው›› የምታድርበት ሆቴል እኮ ሁለቴ ነዋ የመጣሁት ስልክህም ዝግ ነው ..ግራ ሲገባኝ ጊዜዬን ከማባክን እነዚህ ልጆች ልይ ብዬ ወደ እዚህ ጎራ ማለቴ እኮ ነበር..እንጂማ.. ››በማለት ለልጆች ይዞላቸው የመጣውን ቸኮሌት አከፋፈሏቸው ወንበር ስቦ ተቀመጠ ፤አመስግነው ተቀበሉት፡፡
👍68❤8
እጁን ታጠበና ማዕዱን አብሯቸው መቋደሰ ጀመረ... የውብዳር ልታጎርሰው ስትል ‹‹ኧረ እዛው የጀመርሽውን አጉርሺ..››አላት፡፡
‹‹ወደ ቤቴ በመመለሴ ተበሳጨህ እንዴ ?››አለው ሰሎሞን እየሳቀ፡፡
‹‹መበሳጨት አይደለም ....ግን ስርዓትና ደንብ ጣሳችሁ ማለቴ ነው ፡፡እንዲሁ ለሞራላችን
እንኳን የውሸት ሽማግሌ አድርጋችሁን <እኛ ነን
እኮ ያስታረቅናቸው> ብለን ትንሽ ብንጎርር ምን
አለበት…?ደግሞ እኮ ቀጠሮ ስላለን ሁለት ሰዓት ነበር ሆቴልህ የደረስኩት በህልም
አይተሀቸው ነጋ አልነጋ ብለህ ነው እንዴ ዶሮ
ሳይጮኽ የመጣኸው?››
‹‹ኧረ ምን ደሮ ሳይጮኸ ..ወገግ ብሎ ሲነጋ አይኖቼን ስገልጥ እዚሁ ቤት የገዛ መኝታ ቤት ከሙሉ ቤተሰቤ ጋር በአንድ አልጋ ላይ ተኝቼ እራሴን አገኘሁት፡፡››
‹‹ኧረ ባክህ በቃ!!! ለሊት ከተኛህበት አፍነው አምጥተውህ ነዋ፡፡››
‹‹መሰለኝ... እስቲ እሷን ጠይቃት፡፡ >>
‹‹ይሄንን ሁለታችሁንም በተናጥል ለየብቻ ነው የምጠይቃችሁ...አሁን ወደ ውጭ ትወጣለህ ወይስ እዚሁ ነው የምትወለው?››
‹‹ኧረ እወጣለሁ... 5 ሰዓት አንድ የምደርስባት ቦታ አለቺኝ›.እጃቸውን ተጣጥበው ተነሱ፡፡
‹‹እንዴ አባ ለምን ትሄዳለህ? አትሂድ፡፡››
‹‹አልሄድም ... ስራ ደርሼ ልመጣ ነው፡፡››
‹‹ዛሬም እኛ ጋር አዚህ ነው የምታድረው ?>>
‹‹አዎ.. ከአሁን ወዲህ ሁል ግዜ እናንተ ጋር ነው የማድረው ..እዚሁ ነው የምኖረው››አረጋገጠላቸው፡
‹‹እንወድሀለን አባ፡፡›› ሁለቱም በአንድ ላይ ወደ ታች አስጎንብሰውት ግራና ቀኝ ጉንጩን ተከፋፍለው ሳሙትና ሸኙት፡፡
የውብዳር ፈራ ተባ እያለች‹‹ለምሳ ብቅ ትላላችሁ እንዴ?›› ስትል ጠየቀች ፡፡
‹‹አዎ የእሱን አላውቅም እኔ ግን እመጣለሁ..ልክ ስድስት ሰዓት ተኩል ላይ ከች እላለሁ..ያቺ ቡናሽን አፍልተሸ የምትጠብቂኝ ከሆነ?
‹‹ግድ የለህም አንተ ብቻ ና..ሁስ አንተስ..?››አለችው ፈዞ ሁኔታቸውን በትኩረት ሲመለከታቸው የነበረውን ጓደኛቸውን፡፡
‹‹ኧረ እኔ ዛሬ ይዝለለኝ፤ይስፋችሁ >>ብሎ ተሰናበታትና ቀድሞት ወደ መኪናው አመራ.. ሰሎሞንም ተከትሎት የገቢናውን በር ከፍቶ ወደ ውስጥ ሊገባ ሲል የውብ ዳር‹‹ ሶል ››ብላ ተጣራች ፡፡
‹‹ሆቴል ብሄድ እቃዎችህን ይሰጡኛል እንዴ?››
‹‹ግድ የለም እኔ ለምሳ ስመጣ ይዤው እመጣለሁ…ደና ዋይልኝ፡፡››
‹‹እሺ ደህና ዋል››አለችው፡፡
ግቢውን ለቀው እንደወጡ‹‹አንተ ጉደኛ ማታ እርም የሴት ቀሚስ ብገልብ እያልክ ስትምል ስትገዘት አልነበረም እንዴ?››
‹‹ታዲያ መች ገለብኩ?››
<<ማለት?>>
‹‹ማለትማ አዲስ ቀሚስ አልገልብም አልኩህ እንጂ ድሮም የእኔ የነበረውን ቀሚስ አልነካም ብዬ አልማልኩም፡፡››
‹‹አይ አንተ መቼስ ማምለጫ አታጣ....ያም ሆነ ይህ ግን በሆነው ነገር በጣም ደስ ብሎኛል፡፡በተለይ ከልጆችህ አንፃር በዚህ ውሳኔህ ብትፀና እኔ ደስተኛ ነኝ..፡፡››
‹‹በቃ አየውት እኮ .. ሁሉንም ፍላጐቶችህን የምታሟላልህ እንከን አልባ ሴት የትም አታገኝም.. እዚህም ቤት ያለው እሳት መልኩን ቀይሮ እዛም ቤት አለ ፡፡ዋናው ተቻችሎ የአንዱን ጉድለት አንዱ ሞልቶ.. አንዱ ሲያጠፋ
አንዱ ይቅር ብሎ. ህይወትን እየተጋገዙ መኖር ነው..፡፡››
‹‹አሪፍ ነው..ይህቺ እንግዲህ ስሜት ያልነካካት ከህይወት ልምድ የተገኘች ጠቃሚ እውቀት ነች››አለና ለሰሎሞን ንግግር ድጋፍ ሰጠው ፡፡በመጀመሪያ የተጓዙት ሰሎሞን አርፎበት ወደነበረው ሆቴል ነው፤ ዕቃውንም እዛ የቆመችውንም መኪናውን ለመውሰድ፡፡ ደርሰው እንደቆሙ ሁሴን ሞባይሉን አነሳና ደወለ..::
‹‹ሄሎ ፍቅር..አንድ አስደማሚ ወሬ ልነግርሽ ነው››ሰሎሞን አንጓጠጠው፡፡
‹‹ጋዜጠኞች ስትባሉ ወሬ ተቀብሎ በአየር ለመበተን ሚቀድማችሁ የለም..ለምን
አንደኛህን በጋዜጣህ አታሳትመውም፡፡››ብሎት ጥሎት የፎቁን ደረጃ መውጣት ጀመረ፤ሁሴንም ችላ ብሎት ከትንግርት ጋር ማውራቱን ቀጠለ፡፡
‹‹ምንድነው.. ?ምን ሰማህ?››
‹‹ሰሎሞን ነዋ፡፡››
‹‹ሰሎሞን ምን ሆነ?
‹‹ታረቀ እኮ፡››
‹‹አንተ እውነትም ደስ የሚል ቦንብ ወሬ ነው የነገርከኝ... ግን እንደዛ ክርር አድርጋው አልነበር እንዴ እንዴት ሀሳቧን ቀየረች..? ይገርምሀል እኔ እራሴ ከሶስት ቀን በፊት እቤቷ ድረስ ሄጄ ለምኛት ነበር....እንዴት መሰለህ ሲያንዘረዝራት የነበረው...ለማንኛውም እንኳን ታረቁ::>>
‹‹ስለማን ነው የምታወሪው…..?ከየውብዳር ጋር እኮ ነው የታረቁት፡፡››
‹‹የውብ ዳር? >>
‹‹አዎ ከውብዳር ጋር፡፡››
‹‹እንዴት ሆኖ?››
‹‹ዝርዝር መረጃው ገና አልደረሰኝም ግን ያው አደገኛ የፍቅር ግርሻ እንደመጋኛ ሁለቱንም አጠናግሯቸዋል፡፡ >>
‹‹በጣም ደስ ይላል ...በቃ በእናትህ ለምን እራት አንጋብዛቸውም፡፡››
‹‹የት.. ?ቤት ?››
‹‹ቤት እማ ትንሽ ይከብዳል ሆቴል››
‹‹አሪፍ ሀሳብ ነው ... ሰባት ሰዓት አካባቢ ተገናኝተን ስለወጪ መጋራቱ እናውራበታለን፡፡››
‹‹ችግር የለውም ይመቸኛል.. ስትፈልገኝ ቢሮ ና ::>>
‹‹እሺ ቻው ፍቅር፡፡››
‹‹ቻው..አፈቅርሀለሁ፡፡››
‹‹እኔም፡፡››
ስልኩን ዘግቶ ሰሎሞን የሚታገዝ ዕቃ ካለው ሊያግዘው ፎቅ ወደ ሚገኘው መኝታ ክፍሉ የሚወስደውን ደረጃ መውጣት እንደጀመረ ሞባይሉ ጮኸ..መጓዙን ሳያቆም አነሳው‹‹ሄሎ ዶክተር፡፡››
‹‹ሁሴን ሰላም ነህ?››
‹‹ሰላም ነኝ አንቺስ እንዴት ነሽ?››
‹‹ይመስገነው ሰሞኑን ትንሽ የስራ ውጥረት ስለነበረ ነው ላገኝህ ያልቻልኩት.. ዛሬ ከአስራአንድ ሰዓት በኃላ ነፃ ነኝ አንተን የሚመችህ ከሆነ…፡፡››
<<ችግር የለም ይመቸኛል..የት እንገናኝ፡፡››
‹‹ግዮን ቢሆን ይመቸኛል፡፡››
‹‹በቃ እዛው በሰዓቱ እደርሳለሁ፡፡››
‹‹እሺ አመሰግናለሁ ሁሴን፡፡››
‹‹እሺ ቻው ዶ/ር ሶፊያ››
ቤተሰቦች በቅናነት #YouTube #subscribe እያደረጋቹ በጣም ቀንሳችኋል 1ደቂቃ አይፈጅም ገብታችሁ #Subscribe አድርጉ አመሰግናለሁ።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹ወደ ቤቴ በመመለሴ ተበሳጨህ እንዴ ?››አለው ሰሎሞን እየሳቀ፡፡
‹‹መበሳጨት አይደለም ....ግን ስርዓትና ደንብ ጣሳችሁ ማለቴ ነው ፡፡እንዲሁ ለሞራላችን
እንኳን የውሸት ሽማግሌ አድርጋችሁን <እኛ ነን
እኮ ያስታረቅናቸው> ብለን ትንሽ ብንጎርር ምን
አለበት…?ደግሞ እኮ ቀጠሮ ስላለን ሁለት ሰዓት ነበር ሆቴልህ የደረስኩት በህልም
አይተሀቸው ነጋ አልነጋ ብለህ ነው እንዴ ዶሮ
ሳይጮኽ የመጣኸው?››
‹‹ኧረ ምን ደሮ ሳይጮኸ ..ወገግ ብሎ ሲነጋ አይኖቼን ስገልጥ እዚሁ ቤት የገዛ መኝታ ቤት ከሙሉ ቤተሰቤ ጋር በአንድ አልጋ ላይ ተኝቼ እራሴን አገኘሁት፡፡››
‹‹ኧረ ባክህ በቃ!!! ለሊት ከተኛህበት አፍነው አምጥተውህ ነዋ፡፡››
‹‹መሰለኝ... እስቲ እሷን ጠይቃት፡፡ >>
‹‹ይሄንን ሁለታችሁንም በተናጥል ለየብቻ ነው የምጠይቃችሁ...አሁን ወደ ውጭ ትወጣለህ ወይስ እዚሁ ነው የምትወለው?››
‹‹ኧረ እወጣለሁ... 5 ሰዓት አንድ የምደርስባት ቦታ አለቺኝ›.እጃቸውን ተጣጥበው ተነሱ፡፡
‹‹እንዴ አባ ለምን ትሄዳለህ? አትሂድ፡፡››
‹‹አልሄድም ... ስራ ደርሼ ልመጣ ነው፡፡››
‹‹ዛሬም እኛ ጋር አዚህ ነው የምታድረው ?>>
‹‹አዎ.. ከአሁን ወዲህ ሁል ግዜ እናንተ ጋር ነው የማድረው ..እዚሁ ነው የምኖረው››አረጋገጠላቸው፡
‹‹እንወድሀለን አባ፡፡›› ሁለቱም በአንድ ላይ ወደ ታች አስጎንብሰውት ግራና ቀኝ ጉንጩን ተከፋፍለው ሳሙትና ሸኙት፡፡
የውብዳር ፈራ ተባ እያለች‹‹ለምሳ ብቅ ትላላችሁ እንዴ?›› ስትል ጠየቀች ፡፡
‹‹አዎ የእሱን አላውቅም እኔ ግን እመጣለሁ..ልክ ስድስት ሰዓት ተኩል ላይ ከች እላለሁ..ያቺ ቡናሽን አፍልተሸ የምትጠብቂኝ ከሆነ?
‹‹ግድ የለህም አንተ ብቻ ና..ሁስ አንተስ..?››አለችው ፈዞ ሁኔታቸውን በትኩረት ሲመለከታቸው የነበረውን ጓደኛቸውን፡፡
‹‹ኧረ እኔ ዛሬ ይዝለለኝ፤ይስፋችሁ >>ብሎ ተሰናበታትና ቀድሞት ወደ መኪናው አመራ.. ሰሎሞንም ተከትሎት የገቢናውን በር ከፍቶ ወደ ውስጥ ሊገባ ሲል የውብ ዳር‹‹ ሶል ››ብላ ተጣራች ፡፡
‹‹ሆቴል ብሄድ እቃዎችህን ይሰጡኛል እንዴ?››
‹‹ግድ የለም እኔ ለምሳ ስመጣ ይዤው እመጣለሁ…ደና ዋይልኝ፡፡››
‹‹እሺ ደህና ዋል››አለችው፡፡
ግቢውን ለቀው እንደወጡ‹‹አንተ ጉደኛ ማታ እርም የሴት ቀሚስ ብገልብ እያልክ ስትምል ስትገዘት አልነበረም እንዴ?››
‹‹ታዲያ መች ገለብኩ?››
<<ማለት?>>
‹‹ማለትማ አዲስ ቀሚስ አልገልብም አልኩህ እንጂ ድሮም የእኔ የነበረውን ቀሚስ አልነካም ብዬ አልማልኩም፡፡››
‹‹አይ አንተ መቼስ ማምለጫ አታጣ....ያም ሆነ ይህ ግን በሆነው ነገር በጣም ደስ ብሎኛል፡፡በተለይ ከልጆችህ አንፃር በዚህ ውሳኔህ ብትፀና እኔ ደስተኛ ነኝ..፡፡››
‹‹በቃ አየውት እኮ .. ሁሉንም ፍላጐቶችህን የምታሟላልህ እንከን አልባ ሴት የትም አታገኝም.. እዚህም ቤት ያለው እሳት መልኩን ቀይሮ እዛም ቤት አለ ፡፡ዋናው ተቻችሎ የአንዱን ጉድለት አንዱ ሞልቶ.. አንዱ ሲያጠፋ
አንዱ ይቅር ብሎ. ህይወትን እየተጋገዙ መኖር ነው..፡፡››
‹‹አሪፍ ነው..ይህቺ እንግዲህ ስሜት ያልነካካት ከህይወት ልምድ የተገኘች ጠቃሚ እውቀት ነች››አለና ለሰሎሞን ንግግር ድጋፍ ሰጠው ፡፡በመጀመሪያ የተጓዙት ሰሎሞን አርፎበት ወደነበረው ሆቴል ነው፤ ዕቃውንም እዛ የቆመችውንም መኪናውን ለመውሰድ፡፡ ደርሰው እንደቆሙ ሁሴን ሞባይሉን አነሳና ደወለ..::
‹‹ሄሎ ፍቅር..አንድ አስደማሚ ወሬ ልነግርሽ ነው››ሰሎሞን አንጓጠጠው፡፡
‹‹ጋዜጠኞች ስትባሉ ወሬ ተቀብሎ በአየር ለመበተን ሚቀድማችሁ የለም..ለምን
አንደኛህን በጋዜጣህ አታሳትመውም፡፡››ብሎት ጥሎት የፎቁን ደረጃ መውጣት ጀመረ፤ሁሴንም ችላ ብሎት ከትንግርት ጋር ማውራቱን ቀጠለ፡፡
‹‹ምንድነው.. ?ምን ሰማህ?››
‹‹ሰሎሞን ነዋ፡፡››
‹‹ሰሎሞን ምን ሆነ?
‹‹ታረቀ እኮ፡››
‹‹አንተ እውነትም ደስ የሚል ቦንብ ወሬ ነው የነገርከኝ... ግን እንደዛ ክርር አድርጋው አልነበር እንዴ እንዴት ሀሳቧን ቀየረች..? ይገርምሀል እኔ እራሴ ከሶስት ቀን በፊት እቤቷ ድረስ ሄጄ ለምኛት ነበር....እንዴት መሰለህ ሲያንዘረዝራት የነበረው...ለማንኛውም እንኳን ታረቁ::>>
‹‹ስለማን ነው የምታወሪው…..?ከየውብዳር ጋር እኮ ነው የታረቁት፡፡››
‹‹የውብ ዳር? >>
‹‹አዎ ከውብዳር ጋር፡፡››
‹‹እንዴት ሆኖ?››
‹‹ዝርዝር መረጃው ገና አልደረሰኝም ግን ያው አደገኛ የፍቅር ግርሻ እንደመጋኛ ሁለቱንም አጠናግሯቸዋል፡፡ >>
‹‹በጣም ደስ ይላል ...በቃ በእናትህ ለምን እራት አንጋብዛቸውም፡፡››
‹‹የት.. ?ቤት ?››
‹‹ቤት እማ ትንሽ ይከብዳል ሆቴል››
‹‹አሪፍ ሀሳብ ነው ... ሰባት ሰዓት አካባቢ ተገናኝተን ስለወጪ መጋራቱ እናውራበታለን፡፡››
‹‹ችግር የለውም ይመቸኛል.. ስትፈልገኝ ቢሮ ና ::>>
‹‹እሺ ቻው ፍቅር፡፡››
‹‹ቻው..አፈቅርሀለሁ፡፡››
‹‹እኔም፡፡››
ስልኩን ዘግቶ ሰሎሞን የሚታገዝ ዕቃ ካለው ሊያግዘው ፎቅ ወደ ሚገኘው መኝታ ክፍሉ የሚወስደውን ደረጃ መውጣት እንደጀመረ ሞባይሉ ጮኸ..መጓዙን ሳያቆም አነሳው‹‹ሄሎ ዶክተር፡፡››
‹‹ሁሴን ሰላም ነህ?››
‹‹ሰላም ነኝ አንቺስ እንዴት ነሽ?››
‹‹ይመስገነው ሰሞኑን ትንሽ የስራ ውጥረት ስለነበረ ነው ላገኝህ ያልቻልኩት.. ዛሬ ከአስራአንድ ሰዓት በኃላ ነፃ ነኝ አንተን የሚመችህ ከሆነ…፡፡››
<<ችግር የለም ይመቸኛል..የት እንገናኝ፡፡››
‹‹ግዮን ቢሆን ይመቸኛል፡፡››
‹‹በቃ እዛው በሰዓቱ እደርሳለሁ፡፡››
‹‹እሺ አመሰግናለሁ ሁሴን፡፡››
‹‹እሺ ቻው ዶ/ር ሶፊያ››
ቤተሰቦች በቅናነት #YouTube #subscribe እያደረጋቹ በጣም ቀንሳችኋል 1ደቂቃ አይፈጅም ገብታችሁ #Subscribe አድርጉ አመሰግናለሁ።
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍105❤8🔥1👏1
#ተገላቢጦሽ
ያኔ እኮ አብረሃም
ሲኖሮ በዚህ አለም
ሁሉ ተሟልቶለት
ምንም ሳይጎሎበት
ተናግሮ ነበረ
"ለዚች ትንሽ ጊዜ
ለ ስምንት መቶ አመት
ቤትማ አልቀልስም
ድንኳን መች አነሳት"
ዛሬ የሱ ዘሮች
ለሰማንያ አመት
ህንፃውን ገንብተው
ቤታቸውን ሰርተው
ሰፈሩንም አጥረው
ከድሀው ላይ ነጥቀው
.....ይጠባበቃሉ....
ከደጅ የቆመውን
ከዘጠኙ አንዱን፡፡
🎴ዘውዱ እርቅይሁን🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ያኔ እኮ አብረሃም
ሲኖሮ በዚህ አለም
ሁሉ ተሟልቶለት
ምንም ሳይጎሎበት
ተናግሮ ነበረ
"ለዚች ትንሽ ጊዜ
ለ ስምንት መቶ አመት
ቤትማ አልቀልስም
ድንኳን መች አነሳት"
ዛሬ የሱ ዘሮች
ለሰማንያ አመት
ህንፃውን ገንብተው
ቤታቸውን ሰርተው
ሰፈሩንም አጥረው
ከድሀው ላይ ነጥቀው
.....ይጠባበቃሉ....
ከደጅ የቆመውን
ከዘጠኙ አንዱን፡፡
🎴ዘውዱ እርቅይሁን🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍37❤7
#ዝምተኛ_ልቦች
አምነው የወደዱ
ወደው የተካዱ
ተክደው የራዱ
ፍርሃት አንሸራቶ ቁልቁል የጣላቸው
የብቸኛ ልቦች የትነው መውደቂያቸው?
የትነው መድረካቸው?
ማነው አጃቢያቸው?
እንዴት ነው ምታቸው
የተካዱ ልቦች አጋር የራቃቸው
የሚያቀነቅኑት ምንድን ነው ዜማቸው?
የተመረኮዙት እምነት ታጥፎባቸው
ድንገት የወደቁ ፍቅር ያዳጣቸው
ሚስጥር የሚያጋሩት ሰው የበደላቸው
ብቸኝነት ሰርጎ ብቻ ያስቀራቸው
ዝምተኛ ልቦች ምን ይሆን ቋንቋቸው?
ከየት ነው ጥሪያቸው?
በየት ነው ጉዟቸው?
የት ነው መድረሻቸው?
እንደ ሰብአሰገል ጠቅሶ የሚመራቸው
የቃተቱ ልቦች የታል ኮከባቸው?
መቼም ከአምላክ ትንፋሽ ከውሃ ከአፈሩ
ከእምንት እና እውነት ከፍቅር ሲሰሩ
ዝምተኛ ልቦች ጥንቱን ሲፈጥሩ
ተገፍትረው ወድቀው
ደቀው እንዳይቀሩ
በተስፋ ጸንተው ነው ዘላለም ሊኖሩ::
🎴ጌትነት እንየው🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
አምነው የወደዱ
ወደው የተካዱ
ተክደው የራዱ
ፍርሃት አንሸራቶ ቁልቁል የጣላቸው
የብቸኛ ልቦች የትነው መውደቂያቸው?
የትነው መድረካቸው?
ማነው አጃቢያቸው?
እንዴት ነው ምታቸው
የተካዱ ልቦች አጋር የራቃቸው
የሚያቀነቅኑት ምንድን ነው ዜማቸው?
የተመረኮዙት እምነት ታጥፎባቸው
ድንገት የወደቁ ፍቅር ያዳጣቸው
ሚስጥር የሚያጋሩት ሰው የበደላቸው
ብቸኝነት ሰርጎ ብቻ ያስቀራቸው
ዝምተኛ ልቦች ምን ይሆን ቋንቋቸው?
ከየት ነው ጥሪያቸው?
በየት ነው ጉዟቸው?
የት ነው መድረሻቸው?
እንደ ሰብአሰገል ጠቅሶ የሚመራቸው
የቃተቱ ልቦች የታል ኮከባቸው?
መቼም ከአምላክ ትንፋሽ ከውሃ ከአፈሩ
ከእምንት እና እውነት ከፍቅር ሲሰሩ
ዝምተኛ ልቦች ጥንቱን ሲፈጥሩ
ተገፍትረው ወድቀው
ደቀው እንዳይቀሩ
በተስፋ ጸንተው ነው ዘላለም ሊኖሩ::
🎴ጌትነት እንየው🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍40👏6🥰3
እባክሽ አትሂጂ…..
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-13
…
‹‹ያልገባኝ ከስምንት ወንዶች መካከል የተወለድሽ ብቸኛ ሴት ሆነሽ ሳለ እንዴት በአያትሽ እጅ አደግሽ...?ወላጆችሽ እንዴት እሺ ብለው ሰጡሽ ...?››ስል ጠየቅኳት
‹‹እሱ የራሱ የሆነ መራር ታሪክ አለው።ከእኔ በፊት ወላጆቼ ሁለት ሴት ልጆችን ወልደው ነበር፡፡ግን በተወለድ በአንድ ወራቸው ሁለቱም ሞቱ።ከዛ እኔ እንደተወለድኩ አያቴ በሶስተኛው ቀን ከእናቴ እቅፍ ነጠቀችና ወሰደችኝ።ከዛ የራሷን ደረቅ ጡት እያጠባች አሳደገቺኝ።በወቅቱ ወላጆቼ እኔን እንደሌሎቹ ትሞትብናለች የሚል ጥርጣሬ ስለነበራቸው ጨከን ብለው ተይ አትውሰጂያት ማለት አልቻሉም ነበር...በዛ ላይ አያቴ በጣም ተፈሪ ሰው ነበረች።››
‹‹የሚገርም ታሪክ ነው››አልኳት።
እኔ ቢራዬን እየደጋገምኩ እሷ ኮካዋን በዝግታ እየተጎነጨች ጫወታችንን ቀጠልን።
‹‹ግን እምቢ አልሽ እንጂ ወይን ነገር ብትሞክሪ ደስ ይለኝ ነበር፡፡››
‹‹ውይ ዶ/ር ግድ የለህም ይቅርብኝ።››
ሲያንቀዠቅዠኝ‹‹ለምንድነው ግን? ስለማትወጂ ነው?››ስል ጠየቅኳት።
‹‹አይ እንደውም በጣም ነው የምወደው..ግን እኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ወይን እንድቀምስ ያደረገኝ መስፍኔ ነው...ብዙ ጊዜም እጠጣ የነበረው ከእሱ ጋር ነው።እና አሁን እሱ እዛ አልጋ ላይ ተሰትሮ ለነፍሱ ሲታገል .እኔ እዚህ ወይን ልጠጣ ብሞክር ከጉሮሮዬ አይወርድልኝም።››ብላ አስገረመችኝ።ከዛ በምን ሞራሌ ካልጠጣሽ ብዬ ልጫናት እችለው…?የማይሆነውን፡፡.
እኔ በሀሳብ ሰምጬ ስለእሷ እና ባለቤቷ በማሰላሰል ላይ ሳለሁ በመሀል ድምፃን ሰማሁና ከሀሳብ ባነንኩ
‹‹ዶ/ር ለሁለት ነገር ነበር እፈልግሻለሁ ያልከኝ..እንዱን ሰማሁት በጣም ተደስቼያለሁ፡፡ ግን ሁለተኛው ምንድነው?››
ግራ ገባኝ ‹‹የምን ሁለተኛ?››
‹‹እንዴ ዘነጋኸው እንዴ? ለሁለት ነገር ነበር እፈልግሻለሁ ያልከኝ፡፡››
‹‹እ አዎ…ሁለተኛውማ ስለአንቺና መስፍን የፍቅር ታሪክ በቀደም ጀመረሺልኝ ልጆቹ ሲመጡ አቋረጥነው..እና እከዛሬ ሆዴን እንደቆረጠኝ ነው..እባክሽ አሁንእሱን እንድትነግረኝ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹እንዴ.ዶ/ር አሁን?››
‹‹አዎ..አሁን..››
‹‹ሞባይሏን አነሳችና አየች….ቢበዛ 30 ደቂቃ ብቻ ነው መቆየት የምችለው…መስፍኔ ለረጂም ጊዜ ሲያጣኝ ይሳቀቃል፡››
‹‹ገባኝ…በ30 ደቂቃ የቻልሺውን ያህል ንገሪኝና… ቀሪውን ደግሞ ወደሌላ ቀን እናስተላልፈዋልን፡፡››
‹‹እሺ ካልክ ..ግን ምን ላይ ነበር ያቆምኩልህ…››ለማስተዋስ መጣር ጀመረች፡፡
‹‹ እያበጠርሽ የነበረውን ፀጉርሽን እንዳንጨፈረርሽ የሚከራየውን ቤት ልታሳይው ወደክፍሎቹ እየመራሽ ስትወስጂው ነበር ያቆምሺው፡፡
‹‹አንተ..ጥሩ አድማጭ ነህ፡፡››
‹‹አይ ..ያን ያህል እንኳን አይደለሁም ..››
‹‹እንግዲህ እንዳልኩህ ፊት ለፊት እየመራው ወደክፍሎቹ ይዤው ሄድኩ፡፡ክፍሎቹ አንድ አንድ ስርቢስ ክፍል ናቸው፡፡ገብቶ ዞር ዞር እያለ አየውና‹‹ቀጣዩም ክፍል ተመሳሳይ ነው?››ሲል ጠየቀኝ፡፡
በራፍ ላይ እንደቆምኩ‹‹አዎ…ከፈለክ ልክፈትልህና እየው፡፡››አልኩት፡፡
‹‹አይ ተመሳሳይ ከሆነ ይቅርብኝ››
ድንግጥ አልኩ‹‹ምነው አልተመቸህም?አልኩት ››
‹‹አይ ተመሳሳይ ከሆነ ያኛውን ማየቱ አስፈላጊ አይደለም እያልኩሽ ነው››
ተንፈስ አልኩና‹‹እ እንደዛ ነው፡፡››
‹‹አዎ..ግን ስታስቢው የሚሆነኝ ይምስልሻል?››
‹‹አዎ በደንብ ይሆንሀል››አልኩት፡፡
ፍጥጥ ብሎ አየኝና ‹‹እንዴ !የምርሽን ነው?››ሲል ጠየቀኝ፡፡
‹‹አዎ እውነቴን ነው....ቀለሙንም ተላልጦል ካልክ ዛሬውኑ አስቀባልሀለው፡፡››
‹‹እሺ ስፋቱስ?››
‹‹ስፋቱ ይበቃሀል..ሰፊ እኮነው…ለአንድ ሰው ይሄ በጣም በቂ ነው፡፡››
‹‹አንድ ሰው ብቻ እንደሆንኩ በምን አወቅሽ..ሚስት የለኝም ብዬሻለሁ እንዴ?››ብሎ አሳፈረኝም አስደነገጠኝም፡፡
በኩርፊያ መልክ‹‹አይ ሚስት ያለህ ስላልመሰለኝ ነው..ሚስት ካለህ እንኳን ይቅርብህ …ይጠብሀል››አልኩት፡፡
‹‹እሺ ለመሀኑ ኪራዩ ስንት ነው?››
‹‹ሚስት ካለህ ሁለት ሺ ብር..››
ከት ብሎ ሰሳቀና ‹‹እሺ ሚስት ከሌለኝሽ….?››
‹‹ሚስት ከሌለህ ችግር የለውም የፈለከውን መክፈል ትችላለህ፡፡››
‹‹ወደኪሱ ገባና የሆኑ ብሮች አወጣና ቆጠር ቆጠር አድርጎ ከላዩ ላይ አምስት መቶ ብር አጄ ላይ አስቀመጠና‹‹ይሄ ቀብድ ነው.. በቃ ከዛሬ ጀምሮ ይሄንን ክፍል ተከራይቼዋለው…የዛሬ ሳምንት አካባቢ ገባበታለሁ…አሁን ወደጊቢሽ እንዳስገባሺኝ መልሰሽ አስወጪኝ››አለና ክፍሉን ለቆ በመውጣት እንደአመጣጡ ወደውጭ መራመድ ጀመረ ፡፡እኔም ከኃላው ግራ በመጋባት እከተለው ጀመር…››
‹‹ቆይ ግን ከሚስትህ ጋር ነው የምትገባው?››
‹‹እሱን ማወቅ ምን የደረግልሻል..?ሚስቴን ይዤ ከመጣው 2 ሺ ብር ከፍልሻለሁ…እሷን ፈትቼ ብቻዬን ከገባሁ ግን አንድ ሺ ብር ብቻ ነው የምከፍለው››
‹‹እሺ፡፡››
የውጭ በራፉ ጋር እንደደረስን ወደእኔ ዞሮ ትኩር ብሎ በፈገግታ እያየኝ፡፡‹‹ላንቺ ስል ግን ሚስቴን ይዤ ለመምጣት እሞክራለው፡፡››አለኝ፡፡
አበሳጨኝ‹‹እንዴ ሚስትህ ለእኔ ምን ትሰራልኛለች?››
‹‹ብዙ ነገር..አንደኛ እንዳንቺ በጣም ቆንጆ ስለሆነች ጓደኛ ትሆንሻለች…ሁለተኛ ጥሩ የኪራይ ገንዘብ ታገኚያለሽ፡፡››
‹‹አልፈልግም፡፡››
‹‹ምኑ ነው የማትፈልጊው .?.ከሚስቴ ጋር ጓደኛ መሆኑን ወይስ የኪራዩን ብር..?››
‹‹ሁለቱንም…፡፡››
አይኖቹን ከእኔ አሻግሮ ወደውስጥ ተመለከተና ከኃላችን ሰው እንደሌላ ካረጋገጠ በኃላ
‹‹በይ እስከሳምንት ትናፍቂኛለሽ… ደህና ሁኚ ›› ብሎ ጎንበስ በማለት ጉንጬን ሳመኝና ሌላ ምንም ሳይናገር ፊቱን ዞሮ ሄደ፡፡እኔ ግን እጄን ከንፈሩ ያረፈበትን የጉንጬን አካባቢ በፍቅርና በስስት እየዳበስኩ ድንዝዝ ብዬ ለበርካታ ደቂቃዎች ቆምኩ…ከንፈሩ ጉንጬ ላይ ሲያርፍ ልቤ ላይ ነው የሞቀኝ…አእምሮዬን ነው የነዘረኝ…፡፡.
ከዛ ሳምንቱ እንዴት ይለቅ..?ፍፅም ከዛ በፊት ሆኜ የማለቀውን አይነት ሰው ነው የሆንኩት…በአየር ላይ ስንሳፈፍ ከረምኩ..ሚስቱን ይዟት ይመጣ ይሆን…?እውነት እንደእኔ ቆንጆ ነች…?ደግሞ እንደአንቺ ቆንጆ ነች ካለ እኮ የእኔን ቆንጆነት ያምንበታል፡፡ግን ሚስት እያለው ለምን ሳመኝ..?ለምንስ ትናፍቂኛለሽ አለኝ….?በሳምንት ውስጥ ሳባት ኪሎ ያህል ሳልቀንስ አልቀርም፡፡ደግሞ ትክክለኛ የሚመጣበትን ቀንና ሰዓት አልነገረኝም ያም ሌላ ስቃይ ነበር የሆነብኝ፡፡በስምንተኛው ቀን በእለተ እሁድ በአንድ ፒካፕ መኪና አልጋ ፍራሽና የተወሰኑ የቤት እቃዎች ጭኖ ከች አለ፡፡ሮጬ ልጠመጠምበትና አገላብጬ ጉንጮችን ልስማቸው ፈልጌ ነበር፡፡ግን እንደዛ ማድረግ አልቻልኩም፡፡እሱም ሰላም እንኳን አላለኝም..በራፍን እንደከፈትኩላቸው መኪናዋ ወደውስጥ ገብታ እንደቆመች ከገቢናው ወርዶ ወደእኔ እየተመለከተ ያለኝ የመጀመሪያ ነገር ቢኖር…‹‹እቤቴ ቁልፍ ነው ወይስ ክፍት?›› ነበር፡፡
ዝም አልኩት..ክፍት ይሆን ቁልፍ ማስታወስ እንኳን ከበደኝ፡፡
እኔን ተወኝና ከላይ የነበረውን ፍራሹን ይዞ ወደጓሮ ሄደ ፡፡እዛው በረንዳ ላይ ደንዝዤ እንደቆምኩ ነው፡፡ ከሹፌሩ ጋር ተጋግዘው ዕቃውን አጓጉዘው ለመጨረስ15 ደቂቃም የፈጀባቸው አይመስለኝም፡፡ከዛ ወደእኔ ጠጋ አለና ‹‹አያትሽ አሉ..ፈልጌቸው ነበር፡፡››አለኝ፡፡
‹‹የለችም..ቤተክርስቲያን ነች፡፡››
‹‹በቃ..ቁልፍ ካለሽ ቤቱን ቆልፊልኝ››ብሎኝ ብቻ ፊቱን አዞረ፡፡
‹‹ልትሄድ ነው?››
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-13
…
‹‹ያልገባኝ ከስምንት ወንዶች መካከል የተወለድሽ ብቸኛ ሴት ሆነሽ ሳለ እንዴት በአያትሽ እጅ አደግሽ...?ወላጆችሽ እንዴት እሺ ብለው ሰጡሽ ...?››ስል ጠየቅኳት
‹‹እሱ የራሱ የሆነ መራር ታሪክ አለው።ከእኔ በፊት ወላጆቼ ሁለት ሴት ልጆችን ወልደው ነበር፡፡ግን በተወለድ በአንድ ወራቸው ሁለቱም ሞቱ።ከዛ እኔ እንደተወለድኩ አያቴ በሶስተኛው ቀን ከእናቴ እቅፍ ነጠቀችና ወሰደችኝ።ከዛ የራሷን ደረቅ ጡት እያጠባች አሳደገቺኝ።በወቅቱ ወላጆቼ እኔን እንደሌሎቹ ትሞትብናለች የሚል ጥርጣሬ ስለነበራቸው ጨከን ብለው ተይ አትውሰጂያት ማለት አልቻሉም ነበር...በዛ ላይ አያቴ በጣም ተፈሪ ሰው ነበረች።››
‹‹የሚገርም ታሪክ ነው››አልኳት።
እኔ ቢራዬን እየደጋገምኩ እሷ ኮካዋን በዝግታ እየተጎነጨች ጫወታችንን ቀጠልን።
‹‹ግን እምቢ አልሽ እንጂ ወይን ነገር ብትሞክሪ ደስ ይለኝ ነበር፡፡››
‹‹ውይ ዶ/ር ግድ የለህም ይቅርብኝ።››
ሲያንቀዠቅዠኝ‹‹ለምንድነው ግን? ስለማትወጂ ነው?››ስል ጠየቅኳት።
‹‹አይ እንደውም በጣም ነው የምወደው..ግን እኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ወይን እንድቀምስ ያደረገኝ መስፍኔ ነው...ብዙ ጊዜም እጠጣ የነበረው ከእሱ ጋር ነው።እና አሁን እሱ እዛ አልጋ ላይ ተሰትሮ ለነፍሱ ሲታገል .እኔ እዚህ ወይን ልጠጣ ብሞክር ከጉሮሮዬ አይወርድልኝም።››ብላ አስገረመችኝ።ከዛ በምን ሞራሌ ካልጠጣሽ ብዬ ልጫናት እችለው…?የማይሆነውን፡፡.
እኔ በሀሳብ ሰምጬ ስለእሷ እና ባለቤቷ በማሰላሰል ላይ ሳለሁ በመሀል ድምፃን ሰማሁና ከሀሳብ ባነንኩ
‹‹ዶ/ር ለሁለት ነገር ነበር እፈልግሻለሁ ያልከኝ..እንዱን ሰማሁት በጣም ተደስቼያለሁ፡፡ ግን ሁለተኛው ምንድነው?››
ግራ ገባኝ ‹‹የምን ሁለተኛ?››
‹‹እንዴ ዘነጋኸው እንዴ? ለሁለት ነገር ነበር እፈልግሻለሁ ያልከኝ፡፡››
‹‹እ አዎ…ሁለተኛውማ ስለአንቺና መስፍን የፍቅር ታሪክ በቀደም ጀመረሺልኝ ልጆቹ ሲመጡ አቋረጥነው..እና እከዛሬ ሆዴን እንደቆረጠኝ ነው..እባክሽ አሁንእሱን እንድትነግረኝ ነው የምፈልገው፡፡››
‹‹እንዴ.ዶ/ር አሁን?››
‹‹አዎ..አሁን..››
‹‹ሞባይሏን አነሳችና አየች….ቢበዛ 30 ደቂቃ ብቻ ነው መቆየት የምችለው…መስፍኔ ለረጂም ጊዜ ሲያጣኝ ይሳቀቃል፡››
‹‹ገባኝ…በ30 ደቂቃ የቻልሺውን ያህል ንገሪኝና… ቀሪውን ደግሞ ወደሌላ ቀን እናስተላልፈዋልን፡፡››
‹‹እሺ ካልክ ..ግን ምን ላይ ነበር ያቆምኩልህ…››ለማስተዋስ መጣር ጀመረች፡፡
‹‹ እያበጠርሽ የነበረውን ፀጉርሽን እንዳንጨፈረርሽ የሚከራየውን ቤት ልታሳይው ወደክፍሎቹ እየመራሽ ስትወስጂው ነበር ያቆምሺው፡፡
‹‹አንተ..ጥሩ አድማጭ ነህ፡፡››
‹‹አይ ..ያን ያህል እንኳን አይደለሁም ..››
‹‹እንግዲህ እንዳልኩህ ፊት ለፊት እየመራው ወደክፍሎቹ ይዤው ሄድኩ፡፡ክፍሎቹ አንድ አንድ ስርቢስ ክፍል ናቸው፡፡ገብቶ ዞር ዞር እያለ አየውና‹‹ቀጣዩም ክፍል ተመሳሳይ ነው?››ሲል ጠየቀኝ፡፡
በራፍ ላይ እንደቆምኩ‹‹አዎ…ከፈለክ ልክፈትልህና እየው፡፡››አልኩት፡፡
‹‹አይ ተመሳሳይ ከሆነ ይቅርብኝ››
ድንግጥ አልኩ‹‹ምነው አልተመቸህም?አልኩት ››
‹‹አይ ተመሳሳይ ከሆነ ያኛውን ማየቱ አስፈላጊ አይደለም እያልኩሽ ነው››
ተንፈስ አልኩና‹‹እ እንደዛ ነው፡፡››
‹‹አዎ..ግን ስታስቢው የሚሆነኝ ይምስልሻል?››
‹‹አዎ በደንብ ይሆንሀል››አልኩት፡፡
ፍጥጥ ብሎ አየኝና ‹‹እንዴ !የምርሽን ነው?››ሲል ጠየቀኝ፡፡
‹‹አዎ እውነቴን ነው....ቀለሙንም ተላልጦል ካልክ ዛሬውኑ አስቀባልሀለው፡፡››
‹‹እሺ ስፋቱስ?››
‹‹ስፋቱ ይበቃሀል..ሰፊ እኮነው…ለአንድ ሰው ይሄ በጣም በቂ ነው፡፡››
‹‹አንድ ሰው ብቻ እንደሆንኩ በምን አወቅሽ..ሚስት የለኝም ብዬሻለሁ እንዴ?››ብሎ አሳፈረኝም አስደነገጠኝም፡፡
በኩርፊያ መልክ‹‹አይ ሚስት ያለህ ስላልመሰለኝ ነው..ሚስት ካለህ እንኳን ይቅርብህ …ይጠብሀል››አልኩት፡፡
‹‹እሺ ለመሀኑ ኪራዩ ስንት ነው?››
‹‹ሚስት ካለህ ሁለት ሺ ብር..››
ከት ብሎ ሰሳቀና ‹‹እሺ ሚስት ከሌለኝሽ….?››
‹‹ሚስት ከሌለህ ችግር የለውም የፈለከውን መክፈል ትችላለህ፡፡››
‹‹ወደኪሱ ገባና የሆኑ ብሮች አወጣና ቆጠር ቆጠር አድርጎ ከላዩ ላይ አምስት መቶ ብር አጄ ላይ አስቀመጠና‹‹ይሄ ቀብድ ነው.. በቃ ከዛሬ ጀምሮ ይሄንን ክፍል ተከራይቼዋለው…የዛሬ ሳምንት አካባቢ ገባበታለሁ…አሁን ወደጊቢሽ እንዳስገባሺኝ መልሰሽ አስወጪኝ››አለና ክፍሉን ለቆ በመውጣት እንደአመጣጡ ወደውጭ መራመድ ጀመረ ፡፡እኔም ከኃላው ግራ በመጋባት እከተለው ጀመር…››
‹‹ቆይ ግን ከሚስትህ ጋር ነው የምትገባው?››
‹‹እሱን ማወቅ ምን የደረግልሻል..?ሚስቴን ይዤ ከመጣው 2 ሺ ብር ከፍልሻለሁ…እሷን ፈትቼ ብቻዬን ከገባሁ ግን አንድ ሺ ብር ብቻ ነው የምከፍለው››
‹‹እሺ፡፡››
የውጭ በራፉ ጋር እንደደረስን ወደእኔ ዞሮ ትኩር ብሎ በፈገግታ እያየኝ፡፡‹‹ላንቺ ስል ግን ሚስቴን ይዤ ለመምጣት እሞክራለው፡፡››አለኝ፡፡
አበሳጨኝ‹‹እንዴ ሚስትህ ለእኔ ምን ትሰራልኛለች?››
‹‹ብዙ ነገር..አንደኛ እንዳንቺ በጣም ቆንጆ ስለሆነች ጓደኛ ትሆንሻለች…ሁለተኛ ጥሩ የኪራይ ገንዘብ ታገኚያለሽ፡፡››
‹‹አልፈልግም፡፡››
‹‹ምኑ ነው የማትፈልጊው .?.ከሚስቴ ጋር ጓደኛ መሆኑን ወይስ የኪራዩን ብር..?››
‹‹ሁለቱንም…፡፡››
አይኖቹን ከእኔ አሻግሮ ወደውስጥ ተመለከተና ከኃላችን ሰው እንደሌላ ካረጋገጠ በኃላ
‹‹በይ እስከሳምንት ትናፍቂኛለሽ… ደህና ሁኚ ›› ብሎ ጎንበስ በማለት ጉንጬን ሳመኝና ሌላ ምንም ሳይናገር ፊቱን ዞሮ ሄደ፡፡እኔ ግን እጄን ከንፈሩ ያረፈበትን የጉንጬን አካባቢ በፍቅርና በስስት እየዳበስኩ ድንዝዝ ብዬ ለበርካታ ደቂቃዎች ቆምኩ…ከንፈሩ ጉንጬ ላይ ሲያርፍ ልቤ ላይ ነው የሞቀኝ…አእምሮዬን ነው የነዘረኝ…፡፡.
ከዛ ሳምንቱ እንዴት ይለቅ..?ፍፅም ከዛ በፊት ሆኜ የማለቀውን አይነት ሰው ነው የሆንኩት…በአየር ላይ ስንሳፈፍ ከረምኩ..ሚስቱን ይዟት ይመጣ ይሆን…?እውነት እንደእኔ ቆንጆ ነች…?ደግሞ እንደአንቺ ቆንጆ ነች ካለ እኮ የእኔን ቆንጆነት ያምንበታል፡፡ግን ሚስት እያለው ለምን ሳመኝ..?ለምንስ ትናፍቂኛለሽ አለኝ….?በሳምንት ውስጥ ሳባት ኪሎ ያህል ሳልቀንስ አልቀርም፡፡ደግሞ ትክክለኛ የሚመጣበትን ቀንና ሰዓት አልነገረኝም ያም ሌላ ስቃይ ነበር የሆነብኝ፡፡በስምንተኛው ቀን በእለተ እሁድ በአንድ ፒካፕ መኪና አልጋ ፍራሽና የተወሰኑ የቤት እቃዎች ጭኖ ከች አለ፡፡ሮጬ ልጠመጠምበትና አገላብጬ ጉንጮችን ልስማቸው ፈልጌ ነበር፡፡ግን እንደዛ ማድረግ አልቻልኩም፡፡እሱም ሰላም እንኳን አላለኝም..በራፍን እንደከፈትኩላቸው መኪናዋ ወደውስጥ ገብታ እንደቆመች ከገቢናው ወርዶ ወደእኔ እየተመለከተ ያለኝ የመጀመሪያ ነገር ቢኖር…‹‹እቤቴ ቁልፍ ነው ወይስ ክፍት?›› ነበር፡፡
ዝም አልኩት..ክፍት ይሆን ቁልፍ ማስታወስ እንኳን ከበደኝ፡፡
እኔን ተወኝና ከላይ የነበረውን ፍራሹን ይዞ ወደጓሮ ሄደ ፡፡እዛው በረንዳ ላይ ደንዝዤ እንደቆምኩ ነው፡፡ ከሹፌሩ ጋር ተጋግዘው ዕቃውን አጓጉዘው ለመጨረስ15 ደቂቃም የፈጀባቸው አይመስለኝም፡፡ከዛ ወደእኔ ጠጋ አለና ‹‹አያትሽ አሉ..ፈልጌቸው ነበር፡፡››አለኝ፡፡
‹‹የለችም..ቤተክርስቲያን ነች፡፡››
‹‹በቃ..ቁልፍ ካለሽ ቤቱን ቆልፊልኝ››ብሎኝ ብቻ ፊቱን አዞረ፡፡
‹‹ልትሄድ ነው?››
👍57❤7🤔2👏1
‹‹አዎ..ሚስቴ ያቺን የመሰለች ቆንጆ ልጅ ያለችበት ግቢ አልገባም ብላ እያስቸገረችኝ ነው… አሁን እሷን ልለምን እየሄድኩ ነው፡፡እሺ ካለቺኝ ጥሩ ..እምቢ ካለችኝ ግን ይሄ የሆነው በአንቺ ምክንያት ስለሆነ ተመልሼ አንቺኑ ነው የማገባው››ብሎኝ እርምጃውን አፈጠነና መኪና ውስጥ ገብቶ ወጥቶ ሄደ…፡፡
ብላ ከመቀመጫዋ ተነሳች፡፡እኔ በድንዛዜና በተመስጦ እያዳመጥኳት ነበርና፤ በመነሳቷ ግራ ተጋባሁ‹‹ምነው…?››
‹‹.ሰላሳ ደቂቃው አለፈ…ወደቤት ልሄድ..ቀጣዩን ደግሞ ሰሞኑን ነግርሀለው››አለችኝ፡፡
‹‹ልክ እሱ አድርጎሽ እንደነበረው አሁንም አንቺ እኔን እያደረግሽ ነው››ስል አልጎመጎምኩ፡፡
‹‹አይ ዶ/ር..የእሱማ ከምንም አይገጥም ….ጮርቃውን ወጣትነቴን እና የዋህ አፍቃሪነቴን ገና በመጀመሪያው ቀን ተረድቶ ተጫወተብኛል…በል ቸው፡፡››
በዛው ተለያየን፡፡ቀጥታ ወደእማዬ ቤት አመራሁ…..ደግሞ እዛ ምን ይገጥመኝ ይሆን..እርግበ አሁንም እዛ ትሆን ወይስ ወደዘመዶቾ ሄዳለች?
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
ብላ ከመቀመጫዋ ተነሳች፡፡እኔ በድንዛዜና በተመስጦ እያዳመጥኳት ነበርና፤ በመነሳቷ ግራ ተጋባሁ‹‹ምነው…?››
‹‹.ሰላሳ ደቂቃው አለፈ…ወደቤት ልሄድ..ቀጣዩን ደግሞ ሰሞኑን ነግርሀለው››አለችኝ፡፡
‹‹ልክ እሱ አድርጎሽ እንደነበረው አሁንም አንቺ እኔን እያደረግሽ ነው››ስል አልጎመጎምኩ፡፡
‹‹አይ ዶ/ር..የእሱማ ከምንም አይገጥም ….ጮርቃውን ወጣትነቴን እና የዋህ አፍቃሪነቴን ገና በመጀመሪያው ቀን ተረድቶ ተጫወተብኛል…በል ቸው፡፡››
በዛው ተለያየን፡፡ቀጥታ ወደእማዬ ቤት አመራሁ…..ደግሞ እዛ ምን ይገጥመኝ ይሆን..እርግበ አሁንም እዛ ትሆን ወይስ ወደዘመዶቾ ሄዳለች?
ይቀጥላል...
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
❤15👍15
💥💞#አልተዘዋወረችም💥💞
✍ አሌክስ አብርሃም
ክፍል አስራ ሰባት
“እያንዳንዱ ጓደኝነት ውስጥ ትንሽ ትንሽ ጠላትነት አለ!”
ሃይማኖት!
እንደ እኔ መልኳ ብዙም ለማይስብ ሴት፣ ጥሩ አፍቃሪ ማግኜት ከረዥም ዛፍ ላይ በአጭር ቁመት ፍሬ ለማውረድ እንደመሞከር ነው “ሴትነት” ብቻውን በቂ አይደለም፤ ፍሬውን ማውረጃ አንዳች ዘንግ ያስፈልጋል፡፡ ፍሬው ላይ የሚደርስ የትምህርት ፣ የገንዘብ ፣ የጥሩ ምላስ፣ ባለቤት መሆን ያስፈልጋል፤ አልያም ቁመትን የሚያረዝም የጥሩ ቤተሰብ መሰላል ላይ መቆም፡፡ ይኼን ዘንግ በእጄ እስክጨብጥ ስንቱ ያስጎመጄኝ ፍሬ የወፍ ሲሳይ ሆነ፡፡ ተስፋ አስቆራጭ መልክ ነው ያለኝ፡፡ በዚያ ብኩለው በዚህ አስቀያሚነቱ እየባሰበት የሚሄድ፡፡ ምንሽ ነው የሚያስጠላው? ቢሉኝ አላውቅም፤ ግን እንዲሁ መልኬ ቆሜ እያዩኝ እዚያው በቆምኩበት የሚረሳ ዓይነት ነው፡፡ ሰው ካልታወሰ ምኑ ይፈቀራል? የመፈቀር ተቃራኒው መጠላት አይደለም፤ መረሳት ነው፡፡ ማንም የሚያፈቅረውን አይረሳም፤ እኔ ግን ሰዎች አእምሮ ውስጥ በትዝታ መዝገብ እንዳልጻፍ የተረገምኩ ይመስለኛል፡፡ በዚህ እና በሌላ ሌላ ብዙ ምክንያቶች ስለ ራሴ ከማሰብ ይልቅ፣ ስለሌሎች ጉዳይ በማያገባኝ ገብቼ መፈትፈት እወዳለሁ፡፡ ሌሎች ላይ ለመድረስ ሳይሆን ከራሴ ለመሸሽ።
አብሮ አደግ ጓደኛዬ ማኅደረን ጨምሮ የሚቀርቡኝ ሁሉ “ለግጥምና ሥነ-ጽሑፍ ሟች ነሽ' ይሉኛል፣ አይደለሁም። የሚሞትለት ነገር ጠፋ እንዴ? እንዲያውም ግጥም የሚሉትን ነገር አልወድም፤ ምኑም አይጥመኝም፡፡ ግጥም በተለይ ረዥም ግጥም፣ የጅል ለቅሶ ይመስለኛል፡፡ አንዳንድ ገጣሚዎች በአቀራረባቼው እና ቀለል አድርገው በሚያነሱት ሀሳብ ያስቁኛል፣ ሳቅ ማን ይጠላል? በተለይ እኔ ሳቅ በሁለት ምክንያት እወዳለሁ...የመጀመሪያው ሳቅ ያው ሳቅ ስለሆነ ነው፣ ሁለተኛው ግን ጥርስሽ ያምራል ስለሚሉኝ ስስቅ እኩል ሁለት ደስታዎችን ስለማጣጥም ነው፤ በአንድ የሳቅ ጠጠር፣ ሁለት የደስታ ወፍ እንደማውረድ። የሆነ ሆኖ እንደዚያ ዓይነት ግጥሞችን፣ ፍቅረኛዬ ቶማስ ዝርው፣ተራ፣ ገለባ ናቸው ይላቼዋል፡፡ እሱ ራሱ ዝርው ተራና ገለባ የሆነ ልጅ ነበር፡፡ “ትንሽ ካላሳሰቡሽ ምኑን ግጥም ሆኑ?'' የሚለው ነገር አለ (ግድ ካላሰብኩ ብሎ ነገር!) አስበን የምንደርስበትን እዚያው አስበው ፍሬ ነገሩን ከነገሩን ምን አደከመን? ዘመናችን የጥድፊያ ነው፣ ቁጭ ብሎ ለመቆዘም ፋታ አይሰጥም። ሥራችን ነው ካሉ፣ እዚያው ቆዝመውም ይሁን ተጨንቀው፣ ሊሉን የፈለጉትን በአጭርና በግልጽ ቋንቋ ይንገሩን። ቢሆንም ፍቅረኛዬ ቶማስ የተመረቀው በሥነ-ጽሑፍ ምናምን ነውና በዚህ ጉዳይ ገፍቼ አልከራከረውም፡፡ ለነገሩ በምንም ጉዳይ አልከራከረውም። ቶማስ ውስጡ የተቀበረ ቁጭት አለበት፣ ሰዎች ሲጨበጨብላቼው ይበሳጫል። አንዳንዴ ደግሞ ስም የሌለው ገጣሚ በታዋቂዎቹ መካከል ግጥም ሲያቀርብ እና ከተመልካቹ ቀዝቀዝ ያለ ጭብጨባ ሲቼረው፣ ቶማስ ረዢምና ደማቅ ጭብጨባ ያጨበጭባል፣ ሊቆም የሚያዘግመው ጭብጨባ እንደገና ነፍስ ይዘራል፡፡ ቶማስ ለታዋቂ ገጣሚያን ጥላቻ እንዳለበት እረዳለሁ። ገጣሚያን ብቻ ሳይሆን ማንኛውም ታዋቂ ሰው ያበሳጨዋል፤ በተለይ ኢትዮጵያዊ፣ ግን ለምን ብዬ አልጠይቀውም ነበር፡፡ ብዙ ጊዜ ግጥም እንደሚጽፍ ቢነግረኝም፣ በሦስት ዓመት ቆይታችን አንድም _ መስመር ጽፎ ዓይቼ አላውቅም፡፡ _ አይደለምና / ግጥም፣ መደበኛውን መጻፍና ማንበብ መቻሉ እስኪያጠራጥረኝ፣ እጁ ላይ ብዕርም መጽሐፍም ዓይቼ አላውቅም፤ ግድ አይሰጠኝም፡፡
ቶማስ ጋር እንዴት ፍቅረኞች ሆንን? በፍቅሩ ወድቄ ነው? አይደለም፡፡ ፍቅረኛ የሆንበት ብቼኛ ምክንያት ታክሲ ውስጥ ገብቼ ጎኑ ስቀመጥ ገና በወጉ እንኳን ተደላድዬ ሳልቀመጥ “ኦህ! ጥርስሽ እንዴት ያምራል!'' ስላለኝ ብቻ ነው፡፡ ዞር ብዬ አዬሁት፣ ብጉራም ነው እንጂ መልኩ ደህና ነው “አመሰግናለሁ” ብዬ ልዘጋው እቺል ነበር፡፡ ግን በሕይወቴ እንደ ፀሐይ ግርዶሽ በስንት አንድ ጊዜ ያውም ከማያውቀኝ ወንድ የሚሰነዘር አድናቆት እንደ ተራ ነገር ማለፍ የምችል ልጅ አልነበርኩም። አድናቆት ያሳሳኛል፤ የሚያደንቁኝ ሰዎች ጻድቃን ነው የሚመስሉኝ፡፡ ፈገግ ብዬ፣ “ገና ከመግባቴ ...የት አዬኸው ጥርሴን?'' አልኩት፡፡ ይኼ ፈገግታዬ ድፍረት ሰጥቶት ወሬ ጀመርን፡፡ እና ልክ እንደፈላስፎች በቀልድ የሌለውን ፂም እየጎተተ “ታክሲ ውስጥ ከመግባትሽ በፊት ጓደኛሽ ጋር ስትሰነባበች ፈገግ ብለሽ አልነበረምን?'' አለ፡፡ የእውነት አሳቀኝ። እጁን ዘርግቶ “ቶማስ እባላለሁ' አለኝ፡፡ ጨበጥኩት፤ የሴት እጅ እንኳን እንደዚያ አይለሰልስም፡፡ የእጁ ልስላሴ የተለዬ ምቾት ይፈጥራል፡፡ እንዲህ ተዋወቅን፡፡ የዚያን ቀን ስልኬን ሲጠይቀኝ አልከለከልኩትም፤ ግን ይደውላል ብዬ አላስብኩም ነበር፡፡ ላግኝሽ ሲለኝ አልከለከልኩትም፣ግን ቀጥሮኝ ይቀራል ብዬ ፈርቼ ነበር። ልሳምሽ ሲለኝ አልከለከልኩትም፣ ልተኛሽ ሲለኝ አልከለከልኩትም...አብረን የተኛን ቀን አለቀሰ፡፡ እስካሁንም ያ ነገር አንጀቴን ይበላኛል፡፡ እዚህ የጡት ዘር ያልፈጠረበት ባዶ ደረቴ ላይ ተለጥፎ አለቀሰ፡፡ ምንም ነገር ከልክዬው አላውቅም፡፡ እንደማያፈቅረኝ አውቃለሁ፣ እኔም አላፈቅረውም ነበርና ግድ አልነበረኝም። ሥራ አልነበረውም፤ ሳውቀው ጀምሮ ሥራ አልነበረውም። ሥራ ሲፈልግም አይቼው አላውቅም፤ እሱም ያን ያኽል አሳስቦኝ አያውቅም፡፡ እንዲያውም የሻይ እያልኩ በየወሩ የተወሰነ ብር እሰጠው ነበር፡፡ ይኼ ነገር ውለታ ሆኖበት ይሁን ወይም ሌላ መሄጃ ስለሌለው እንጃ እስከ መጨረሻው ከእኔ ጋር ነበር፡፡
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሥነጽሑፍ ተመርቆ ለሦስት ዓመት ሥራ ሳያገኝ ቆይቷል፡፡ እንዴት እንደሚኖር ለራሴም ይገርመኛል፡፡ግን ጠይቄው አላውቅም፡፡ እየቆዬ ሲገባኝ እሱም ከእኔ በባሰ ሁኔታ የተገፋና በራስ መተማመኑ የተንኮታኮተ ልጅ ነበር፡፡ ልዩነታችን ይኼን መገፋታችንን የተቀበልንበት መንገድ ላይ ነበር፡፡ እኔ ወደ ውስጤ ኖርኩት፤ እሱ በጥላቻ፣ በጠብ፣ በማማረር እና ሌሎችን በማናናቅ ኖረው። መሠረታዊ ችግራችን ግን ያው መገፋት ነበር፡፡ ከጓደኛዬ ማኅደረ ሰላም ፍቅረኛ አብርሃም ውጭ ቶማስን የሚወደው ይቅርና አብሮት ለደቂቃዎች መቀመጥ የሚፈልግ አንድም ሰው አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡ የሰው ዘር በሙሉ ክንፍ ያለው መልአክ ነው ብላ ልትከራከር የሚቃጣት ጓደኛዬ ማኅደረ እንኳን ቶማስን አትወደውም ነበር፡፡ “አልፈሽ ልትወጂው ብትሞክሪ እንኳን ዙሪያውን በእሾህ አጥር የታጠረ ልጅ ነው፣ በዬት ሽንቁር አልፈሽ እንደወደድሽው እንጃልሽ'' ትለኛለች፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰው ጋር ነው የኖርኩት። “በፍቅር”፡፡ የሆነ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የሥነ-ጽሑፍ ዝግጅት ላይ እንደ ፍቅረኛ ክንዴን ይዞ የወሰደኝ ቶማስ ነበር። ለእኔ ይኼ ማለት ብዙ ነገር ነው፡፡ ለቅሶ ቤት ይውሰደኝ፣ ሰርግ ቤት ጉዳዬ አልነበረም፤ ሳያፍርብኝ እጄን ይዞ ሰው መኻል የሚገኝ ሰው ከጎኔ መኖሩ ብቻውን የሚሰጠኝ ስሜት የተለዬ ነበር። ከዚያ በኋላ ብዙ የሥነ-ጽሑፍና የግጥም ዝግጅቶች ላይ ቶማስ ጋርም ይሁን ብቻዬን እገኝ ነበር። እንዲሁ የግጥም ምሽቶች ላይ መገኜት የሆነ ዘመናዊነት ነገር አለው አይደል?! የሥዕል ኤግዝቢሽን፣ የሥነ-ጽሑፍ ምሽት ምናምን? በተለይ “ምሽት'' የሚለው ደስ ይላል። "Maslow's hierarchy of needs" እንደሚነግረን የሰው ልጅ የዕለት ጉርሱን የዓመት ልብሱን ካገኜ በኋላ ጥጋብና ብርዱን ከመከላከል ባለፈ የመታዬት፣ የመወደድ ፍላጎቱን ለማርካት ይታትራል። ምንም ደሃ አገር ብንኖር
✍ አሌክስ አብርሃም
ክፍል አስራ ሰባት
“እያንዳንዱ ጓደኝነት ውስጥ ትንሽ ትንሽ ጠላትነት አለ!”
ሃይማኖት!
እንደ እኔ መልኳ ብዙም ለማይስብ ሴት፣ ጥሩ አፍቃሪ ማግኜት ከረዥም ዛፍ ላይ በአጭር ቁመት ፍሬ ለማውረድ እንደመሞከር ነው “ሴትነት” ብቻውን በቂ አይደለም፤ ፍሬውን ማውረጃ አንዳች ዘንግ ያስፈልጋል፡፡ ፍሬው ላይ የሚደርስ የትምህርት ፣ የገንዘብ ፣ የጥሩ ምላስ፣ ባለቤት መሆን ያስፈልጋል፤ አልያም ቁመትን የሚያረዝም የጥሩ ቤተሰብ መሰላል ላይ መቆም፡፡ ይኼን ዘንግ በእጄ እስክጨብጥ ስንቱ ያስጎመጄኝ ፍሬ የወፍ ሲሳይ ሆነ፡፡ ተስፋ አስቆራጭ መልክ ነው ያለኝ፡፡ በዚያ ብኩለው በዚህ አስቀያሚነቱ እየባሰበት የሚሄድ፡፡ ምንሽ ነው የሚያስጠላው? ቢሉኝ አላውቅም፤ ግን እንዲሁ መልኬ ቆሜ እያዩኝ እዚያው በቆምኩበት የሚረሳ ዓይነት ነው፡፡ ሰው ካልታወሰ ምኑ ይፈቀራል? የመፈቀር ተቃራኒው መጠላት አይደለም፤ መረሳት ነው፡፡ ማንም የሚያፈቅረውን አይረሳም፤ እኔ ግን ሰዎች አእምሮ ውስጥ በትዝታ መዝገብ እንዳልጻፍ የተረገምኩ ይመስለኛል፡፡ በዚህ እና በሌላ ሌላ ብዙ ምክንያቶች ስለ ራሴ ከማሰብ ይልቅ፣ ስለሌሎች ጉዳይ በማያገባኝ ገብቼ መፈትፈት እወዳለሁ፡፡ ሌሎች ላይ ለመድረስ ሳይሆን ከራሴ ለመሸሽ።
አብሮ አደግ ጓደኛዬ ማኅደረን ጨምሮ የሚቀርቡኝ ሁሉ “ለግጥምና ሥነ-ጽሑፍ ሟች ነሽ' ይሉኛል፣ አይደለሁም። የሚሞትለት ነገር ጠፋ እንዴ? እንዲያውም ግጥም የሚሉትን ነገር አልወድም፤ ምኑም አይጥመኝም፡፡ ግጥም በተለይ ረዥም ግጥም፣ የጅል ለቅሶ ይመስለኛል፡፡ አንዳንድ ገጣሚዎች በአቀራረባቼው እና ቀለል አድርገው በሚያነሱት ሀሳብ ያስቁኛል፣ ሳቅ ማን ይጠላል? በተለይ እኔ ሳቅ በሁለት ምክንያት እወዳለሁ...የመጀመሪያው ሳቅ ያው ሳቅ ስለሆነ ነው፣ ሁለተኛው ግን ጥርስሽ ያምራል ስለሚሉኝ ስስቅ እኩል ሁለት ደስታዎችን ስለማጣጥም ነው፤ በአንድ የሳቅ ጠጠር፣ ሁለት የደስታ ወፍ እንደማውረድ። የሆነ ሆኖ እንደዚያ ዓይነት ግጥሞችን፣ ፍቅረኛዬ ቶማስ ዝርው፣ተራ፣ ገለባ ናቸው ይላቼዋል፡፡ እሱ ራሱ ዝርው ተራና ገለባ የሆነ ልጅ ነበር፡፡ “ትንሽ ካላሳሰቡሽ ምኑን ግጥም ሆኑ?'' የሚለው ነገር አለ (ግድ ካላሰብኩ ብሎ ነገር!) አስበን የምንደርስበትን እዚያው አስበው ፍሬ ነገሩን ከነገሩን ምን አደከመን? ዘመናችን የጥድፊያ ነው፣ ቁጭ ብሎ ለመቆዘም ፋታ አይሰጥም። ሥራችን ነው ካሉ፣ እዚያው ቆዝመውም ይሁን ተጨንቀው፣ ሊሉን የፈለጉትን በአጭርና በግልጽ ቋንቋ ይንገሩን። ቢሆንም ፍቅረኛዬ ቶማስ የተመረቀው በሥነ-ጽሑፍ ምናምን ነውና በዚህ ጉዳይ ገፍቼ አልከራከረውም፡፡ ለነገሩ በምንም ጉዳይ አልከራከረውም። ቶማስ ውስጡ የተቀበረ ቁጭት አለበት፣ ሰዎች ሲጨበጨብላቼው ይበሳጫል። አንዳንዴ ደግሞ ስም የሌለው ገጣሚ በታዋቂዎቹ መካከል ግጥም ሲያቀርብ እና ከተመልካቹ ቀዝቀዝ ያለ ጭብጨባ ሲቼረው፣ ቶማስ ረዢምና ደማቅ ጭብጨባ ያጨበጭባል፣ ሊቆም የሚያዘግመው ጭብጨባ እንደገና ነፍስ ይዘራል፡፡ ቶማስ ለታዋቂ ገጣሚያን ጥላቻ እንዳለበት እረዳለሁ። ገጣሚያን ብቻ ሳይሆን ማንኛውም ታዋቂ ሰው ያበሳጨዋል፤ በተለይ ኢትዮጵያዊ፣ ግን ለምን ብዬ አልጠይቀውም ነበር፡፡ ብዙ ጊዜ ግጥም እንደሚጽፍ ቢነግረኝም፣ በሦስት ዓመት ቆይታችን አንድም _ መስመር ጽፎ ዓይቼ አላውቅም፡፡ _ አይደለምና / ግጥም፣ መደበኛውን መጻፍና ማንበብ መቻሉ እስኪያጠራጥረኝ፣ እጁ ላይ ብዕርም መጽሐፍም ዓይቼ አላውቅም፤ ግድ አይሰጠኝም፡፡
ቶማስ ጋር እንዴት ፍቅረኞች ሆንን? በፍቅሩ ወድቄ ነው? አይደለም፡፡ ፍቅረኛ የሆንበት ብቼኛ ምክንያት ታክሲ ውስጥ ገብቼ ጎኑ ስቀመጥ ገና በወጉ እንኳን ተደላድዬ ሳልቀመጥ “ኦህ! ጥርስሽ እንዴት ያምራል!'' ስላለኝ ብቻ ነው፡፡ ዞር ብዬ አዬሁት፣ ብጉራም ነው እንጂ መልኩ ደህና ነው “አመሰግናለሁ” ብዬ ልዘጋው እቺል ነበር፡፡ ግን በሕይወቴ እንደ ፀሐይ ግርዶሽ በስንት አንድ ጊዜ ያውም ከማያውቀኝ ወንድ የሚሰነዘር አድናቆት እንደ ተራ ነገር ማለፍ የምችል ልጅ አልነበርኩም። አድናቆት ያሳሳኛል፤ የሚያደንቁኝ ሰዎች ጻድቃን ነው የሚመስሉኝ፡፡ ፈገግ ብዬ፣ “ገና ከመግባቴ ...የት አዬኸው ጥርሴን?'' አልኩት፡፡ ይኼ ፈገግታዬ ድፍረት ሰጥቶት ወሬ ጀመርን፡፡ እና ልክ እንደፈላስፎች በቀልድ የሌለውን ፂም እየጎተተ “ታክሲ ውስጥ ከመግባትሽ በፊት ጓደኛሽ ጋር ስትሰነባበች ፈገግ ብለሽ አልነበረምን?'' አለ፡፡ የእውነት አሳቀኝ። እጁን ዘርግቶ “ቶማስ እባላለሁ' አለኝ፡፡ ጨበጥኩት፤ የሴት እጅ እንኳን እንደዚያ አይለሰልስም፡፡ የእጁ ልስላሴ የተለዬ ምቾት ይፈጥራል፡፡ እንዲህ ተዋወቅን፡፡ የዚያን ቀን ስልኬን ሲጠይቀኝ አልከለከልኩትም፤ ግን ይደውላል ብዬ አላስብኩም ነበር፡፡ ላግኝሽ ሲለኝ አልከለከልኩትም፣ግን ቀጥሮኝ ይቀራል ብዬ ፈርቼ ነበር። ልሳምሽ ሲለኝ አልከለከልኩትም፣ ልተኛሽ ሲለኝ አልከለከልኩትም...አብረን የተኛን ቀን አለቀሰ፡፡ እስካሁንም ያ ነገር አንጀቴን ይበላኛል፡፡ እዚህ የጡት ዘር ያልፈጠረበት ባዶ ደረቴ ላይ ተለጥፎ አለቀሰ፡፡ ምንም ነገር ከልክዬው አላውቅም፡፡ እንደማያፈቅረኝ አውቃለሁ፣ እኔም አላፈቅረውም ነበርና ግድ አልነበረኝም። ሥራ አልነበረውም፤ ሳውቀው ጀምሮ ሥራ አልነበረውም። ሥራ ሲፈልግም አይቼው አላውቅም፤ እሱም ያን ያኽል አሳስቦኝ አያውቅም፡፡ እንዲያውም የሻይ እያልኩ በየወሩ የተወሰነ ብር እሰጠው ነበር፡፡ ይኼ ነገር ውለታ ሆኖበት ይሁን ወይም ሌላ መሄጃ ስለሌለው እንጃ እስከ መጨረሻው ከእኔ ጋር ነበር፡፡
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሥነጽሑፍ ተመርቆ ለሦስት ዓመት ሥራ ሳያገኝ ቆይቷል፡፡ እንዴት እንደሚኖር ለራሴም ይገርመኛል፡፡ግን ጠይቄው አላውቅም፡፡ እየቆዬ ሲገባኝ እሱም ከእኔ በባሰ ሁኔታ የተገፋና በራስ መተማመኑ የተንኮታኮተ ልጅ ነበር፡፡ ልዩነታችን ይኼን መገፋታችንን የተቀበልንበት መንገድ ላይ ነበር፡፡ እኔ ወደ ውስጤ ኖርኩት፤ እሱ በጥላቻ፣ በጠብ፣ በማማረር እና ሌሎችን በማናናቅ ኖረው። መሠረታዊ ችግራችን ግን ያው መገፋት ነበር፡፡ ከጓደኛዬ ማኅደረ ሰላም ፍቅረኛ አብርሃም ውጭ ቶማስን የሚወደው ይቅርና አብሮት ለደቂቃዎች መቀመጥ የሚፈልግ አንድም ሰው አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡ የሰው ዘር በሙሉ ክንፍ ያለው መልአክ ነው ብላ ልትከራከር የሚቃጣት ጓደኛዬ ማኅደረ እንኳን ቶማስን አትወደውም ነበር፡፡ “አልፈሽ ልትወጂው ብትሞክሪ እንኳን ዙሪያውን በእሾህ አጥር የታጠረ ልጅ ነው፣ በዬት ሽንቁር አልፈሽ እንደወደድሽው እንጃልሽ'' ትለኛለች፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰው ጋር ነው የኖርኩት። “በፍቅር”፡፡ የሆነ ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ የሥነ-ጽሑፍ ዝግጅት ላይ እንደ ፍቅረኛ ክንዴን ይዞ የወሰደኝ ቶማስ ነበር። ለእኔ ይኼ ማለት ብዙ ነገር ነው፡፡ ለቅሶ ቤት ይውሰደኝ፣ ሰርግ ቤት ጉዳዬ አልነበረም፤ ሳያፍርብኝ እጄን ይዞ ሰው መኻል የሚገኝ ሰው ከጎኔ መኖሩ ብቻውን የሚሰጠኝ ስሜት የተለዬ ነበር። ከዚያ በኋላ ብዙ የሥነ-ጽሑፍና የግጥም ዝግጅቶች ላይ ቶማስ ጋርም ይሁን ብቻዬን እገኝ ነበር። እንዲሁ የግጥም ምሽቶች ላይ መገኜት የሆነ ዘመናዊነት ነገር አለው አይደል?! የሥዕል ኤግዝቢሽን፣ የሥነ-ጽሑፍ ምሽት ምናምን? በተለይ “ምሽት'' የሚለው ደስ ይላል። "Maslow's hierarchy of needs" እንደሚነግረን የሰው ልጅ የዕለት ጉርሱን የዓመት ልብሱን ካገኜ በኋላ ጥጋብና ብርዱን ከመከላከል ባለፈ የመታዬት፣ የመወደድ ፍላጎቱን ለማርካት ይታትራል። ምንም ደሃ አገር ብንኖር
👍41❤8
ያለችንን ለማሳዬት ጥምቀትን መጠበቅ የለብንም። መቼም እንዲህ እንዲህ ያሉት ቦታዎች እንይ ብሎ ለመታዬት የሚሄደው ባይበዛ ነው? ምኔ ነው ተረት ተረት? ምኔ ነው ግጥም? ምኔ ነው ሐሳብ? ጥበብ ቅብርጥስ...እነዚያ በቁማቼው ጫጭተው፣
የተላመጠ የወይራ መፋቂያ ከመሰሉ ገጣሚ ተብዬዎች ምን ጠብ ሊል?...ተጠበ ተጨንቆ ትልቅ ሥራ እንደሠራ ሰው ከመድረክ ወርደው ሲጋራቼውን በላይ በላዩ ሲያቦኑ እና መጠጣቼውን ሲገለብጡ ደሜ ይፈላል፡፡ በእርግጥ ከፍቅረኛዬ ቶማስ ይሻላሉ፤ እሱ እንዲሁ በመቆዘም ብቻ፤ ደክሞ የሚውልና የሚያድር ድብርታም ነበር። ሲጋራና መጠጡም አይቀርበት፡፡ አንድም ቀን ይኼን ሱስህን ቀንስ አልያም አቁም ብዬው ግን አላውቅም፡፡ እንዲያውም የሚያስፈልገውን ገንዘብ እሰጠው ነበር፡፡ ሳንባውና ጉበቱ ከስሎ ቢሞት ግድ አልነበረኝም፡ በእነዚህ ምሽቶች ከብዙ ታዋቂ ደራሲ እና ገጣሚ ሰዓሊ እና ምንትሶች ጋር ተዋውቂያለሁ። የብዙዎቹ መጽሐፎች አሉኝ፡፡ አብሮ ሻይ ቡና ማለቱ ከተራው ሕይወት ትንሽ ከፍ የማለት ስሜት አለው፤ አለ አይደል በቀጥታም ባይሆን “እንትናን አውቀዋለሁኮ!”… “ኧረ ባክሽ? ይኼ እንትን ፊልም የጻፈው? የእንትን መጽሐፍ ደራሲ" ...መባባል የሆነ ስሜት አለው፡፡ በተለይ ለእኔ ብዙ ነው ትርጉሙ፤ ሰው ከማያውቀው ሕመሜ ባይፈውሰኝም እንዳገግም ረድቶኛል፡፡ መልከ ጥፉ ነኝ፣ እራሴን ጠንቅቄ አውቃለሁ። መልኬ ወንዶችን አይስብም። ከእግሮቼና ከጥርሴ በስተቀር ምኔም ምኔም ዕይታ አይስብም፡፡ በእርግጥ ጓደኛዬ ማኅደረ ዓይኖችሽ ያምራሉ ትለኛለች፡፡ ሌላ ሰው ማንም ብሎኝ ስለማያውቅ እርግጠኛ አይደለሁም። ማኅደረ፣ ርግብ ነችና እባብም ቆንጆ ሆኖ የሚታያት ፍጥረት ነች፡፡ ለእሷ የሰው ልጅ በሙሉ ቆንጆ ነው፡፡ የኾነ ሆኖ አላምርምና ዕድሌ ነው ፤ ዓለም የቆንጆዎች ናት ብዬ ቁጭ ልል አልችልም፡፡ እዚሀ አስቀያሚ ሌጣ ደረቴ ውስጥ ያለው ልቤ ሥራው ደም መርጨት ብቻ አይደለምና እንደ ሰው የሚወደኝ የሚያፈቅረኝ ሰው እፈልጋለሁ። ሁልጊዜ ፍቅር እፈልጋለሁ፡፡ ዓይኖቼ ወንዶች ላይ እንደተንከራተቱ ናቸው፡፡ ግን ከ “ሃይስኩል” እስከ ኮሌጅ ፍቅረኛ ኖሮኝ አያውቅም። አደባባይ ላይ ተቁሞ ኡኡ... | የወንድ ያለኽ አይባል ነገር፡፡ ይኼ መገፋት ወደ ትምህርት ገፍቶኝ “ውይ እሷ እንደ
ወጣት አትልከሰከስ ትምህርቷ ላይ ብቻ...'' የሚባልልኝ ጎበዝ ተማሪ ሆንኩ፡፡ (ልልከስከስስ ብል...) ከዚያ በተረፈኝ ጊዜ ቤተክርስቲያን አዘወትራለሁ፡፡ ይኼም የጨዋነት ደረጃዬን ከፍ አደረገልኝ፡፡ የልቤን ናፍቆት ግን ማንም አያውቅም ነበር፡፡ እንዱ ይኼን ወረቀትሽን ወደዚያ ጣይና አግብቼ ልውሰድሽ ቢለኝ፣ ወደዚያ ወርውሬ እከተለው ነበር፡፡ በነጠላ የተሸፈነውም፣ በ'ሚንስከርት' ቡጊ ቡጊ የሚል ልቤ ነበር፡፡ ይገርመኛል ታዲያ፤ ከእህት በላይ የምታውቀኝ ጓደኛዬ ማኅደረን ጨምሮ የሚያውቁኝ ሁሉ የሚያስቡኝ ከዚህ በጣም አርቀው መሆኑ። እንዴት ዓይነት ማስመሰል ብከናነብ ነው? እላለሁ ለራሴ፡፡ ድፍን ወዳጅ ዘመዶቼ በአለፍ ገደም የሚያውቁኝ ሁሉ “ስለ ሃይሚ ጨዋነት በዐሥር ጣታችን እንፈርማለን!" ይላሉ። ከመፈረማችሁ በፊት ... በእርግጥ እንዲህ ስል ወንድ አላውቅም ማለቴ አልነበረም፡፡ አሳፋሪ ቢሆንም ወንድ ጋር መተኛት የጀመርኩት ገና የዐሥረኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ነው፡፡ ይኼንን ማንም አያውቅም ማኅደረን ጨምሮ።ምን ተብሎ ይነገራል!? የጎረቤታችን የእትዬ ሆህተ ባለቤት ጋሽ ዓለምነህ ጋር ተኛሁ ተብሎ? ለመጀመሪያ ጊዜ ወሲብ የፈጸምኩት እሱ ጋር ነበር፤ ረዥም ቀይ ነው፡፡ ለምን እንደሆነ እንጃ ሳዬው ዶክተር ነበር የሚመስለኝ፣ ኧረ ነጋዴ ነው ተብዬ ሁሉ ዶክተር ነበር የሚመስለኝ፡፡ አብረን እንድንተኛ ሲጠይቀኝ አልተግደረደርኩም(ጠዬቀኝ እንኳን አይባልም) እንዲያውም የሆነ ትልቅ ክብር ነበር የተሰማኝ። እትዬ ሆሀተ “እመብርሃንን የመሰለች" የሚባልላት ቆንጆ ሴት ነበረች፡፡ በፊልም የምናያቸውን የሀንድ ሴት ተዋናያን የመሰለች። በሙያዋ እዚህ ልደታ ፍርድ ቤት ዳኛ ነች፡፡ ሁሉም ሰው እትዬ ይላታል እንጂ፣ ያኔ ዕድሜዋ ከሰላሳ መብለጡን እንጃ፡፡ ታዲያ ባለቤቷ ጋሽ ዓለምነህን (ዓለምዬ ነዉ የምትለው) ከትምህርት ቤታችን ወረድ ብሎ የሕንፃ መሣሪያዎች መሸጫ መደብር ነበረው፣ ነጋዴ ነው፡፡ እኔና ማኅደረ ከትምህርት ቤት ወጥተን ወደ ቤታችን ስናዘግም ድንገት ከተገጣጠምን ያቺን ነጭ
ቶዮታ ኮሮላውን ያቆምና “ኑ! ግቡ'' ይለናል፡፡ እየተሸኮረመምን አንቺ ቅደሚ፣ አንቺ እየተባባልን እንገባለን፣ ይሸኜናል፡፡ ማኅደረን ሜክሲኮ ጫፍ ላይ ካወረዳት በኋላ፣ እኔ ጋር አንድ ሰፈር ስለሆንን እንቀጥላለን፡፡ ብዙ ብዙ የሚያስቅ ነገር እያወራኝ፤ ብዙ ብዙ የሚገባኝንና የማይገባኝን የሥራ ጉዳይ ምናምን እያወራኝ ...ልክ እንደ ጓደኛዉ፣ ውስጤ በጣም ነበር የሚወደው፡፡ እንደዚያም ሆኖ በኋላ መመልከቻ መስተዋቱ ደጋግሞ ዓይኑን ጣል እያደረገ ሲመለከት ብዙ ጊዜ ዓይኖቻችን ቢገጣጠሙም፤ ያው እንደሁሉም ወንድ ማኅደረን ለአጓጉል ነገር የፈለጋት ነበር የመሰለኝ፡፡ ዓይኔ ንቁ ነው። እንዲያውም ማኅደረን በኋላ “ምንድን ነው ባለትዳር አይደል እንዴ? ዐሥር ጊዜ ያፈጥብሻል"አልኳት፡፡ ደንገጥ ብላ “አፈጠጠ እንዴ?...አላዬሁትም'' አለች፡፡ ሁልጊዜ የሷን ወንዶች የማዬው እኔ ነኝ፡፡ እንዲህ ሲሆን ልለምደው ያልቻልኩት ብስጭት ውስጤ ይፈነዳል፡፡ ደንገጡር የሆንኩ ዓይነት። ማኅደረ ጋር የሚያገኙን ወንዶች ሁሉ ከመጀመሪያዋ ሰላምታ በኋላ ከነመፈጠሬ እንደረሱኝ ነው “የት ነው የምትማሩት? ...ስንተኛ ክፍል ናችሁ?...የት እየሄዳችሁ ነው? ..." የሚሉ ጥያቄዎች ሁሉ እኔን ማጀቢያ አድርገው ለማኅደረ የሚቀርቡ ነበሩ፡፡ ጥያቄያቼውን የምመልሰው እንደ አስተርጓሚ እኔ ነበርኩ፡፡ ማኅደረ ሲበዛ ዝምተኛ ናትና የእሷ አንደበት ነበርኩ፡፡ እኔ እየመለስኩ የእሷን ዓይን ለማዬት የሚታገሉት ነገር ያበሳጨኛል፤ምንም ልበል ግድ አልነበራቼውም “ራሴን ላጠፋ እየሄድኩ ነው'' ብላቼው ራሱ ግድ የሚሰጣቼው አይመስለኝም። ታዲያ አንድ ቀን ማኅደረ አባቷ ታመው፣ ከትምህርት ቤት ቀርታ ብቻዬን ታክሲ ስጠብቅ የጋሽ ዓለምነህን መኪና ከሰፈር ስትመጣ አዬኋት፡፡ ብቻዬን ስለሆንኩ እንዳላዬ ያልፈኛል ብዬ እኔም ያላዬሁት ለመምሰል እዚህና እዚያ ዓይኔን ሳቃብዝ፣ ያቺን መኪናውን ፊት ለፊቴ አቆመና መስተዋቱን ዝቅ አድርጎ “ሃይማኖት” ብሎ ጠራኝ፡፡ ታክሲ የሚጠብቀው ሰው ሁሉ ስሙ ሃይማኖት ይመስል ሁሉም ወደ እሱ
ዞረ። በእጁ ምልካት ወደ መኪናው እንድገባ ጠራኝ፣አባቴ ነበር የሚመስለው.. አላንገራገርኩም፣ የኋላውን በር ልከፍት ስታገል...ነይ እዚህ ብሎ ተንጠራርቶ የጋቢናውን በር ከፈተልኝ፡፡ ትንንሽ ነገሮች አሉ ምናልባት ለሌሎች ምንም የሆኑ፡፡ ለእኔ ግን ያች ቅጽበት የንግሥና ዙፋን ላይ የመቀመጥ ያኽል ልዩ የመከበር ስሜት ነበራት፡፡ ሁልጊዜ ይቺን የጋሽ ዓለምነህ ቶዮታ ኮሮላ መኪና ሰፈር ውስጥ በተለይ ማታ ላይ ሳያት፣ ሚስቱ እትዬ ሆህተ በክብር፣ ያኔ እኔ የተቀመጥኩበት ቦታ ላይ ተቀምጣ ነበር የማያት፡፡ ወደ ፊት የሚወደኝን ሰው አግብቼ እያልኩ የምመኜው ምኞት፣ በዚያ መስታወት አልፎ በዓይኔ የተፀነሰ ምቾት ነበር፡፡ በዚያ ላይ መኪናውን የሞላው ሽቶ...
የተላመጠ የወይራ መፋቂያ ከመሰሉ ገጣሚ ተብዬዎች ምን ጠብ ሊል?...ተጠበ ተጨንቆ ትልቅ ሥራ እንደሠራ ሰው ከመድረክ ወርደው ሲጋራቼውን በላይ በላዩ ሲያቦኑ እና መጠጣቼውን ሲገለብጡ ደሜ ይፈላል፡፡ በእርግጥ ከፍቅረኛዬ ቶማስ ይሻላሉ፤ እሱ እንዲሁ በመቆዘም ብቻ፤ ደክሞ የሚውልና የሚያድር ድብርታም ነበር። ሲጋራና መጠጡም አይቀርበት፡፡ አንድም ቀን ይኼን ሱስህን ቀንስ አልያም አቁም ብዬው ግን አላውቅም፡፡ እንዲያውም የሚያስፈልገውን ገንዘብ እሰጠው ነበር፡፡ ሳንባውና ጉበቱ ከስሎ ቢሞት ግድ አልነበረኝም፡ በእነዚህ ምሽቶች ከብዙ ታዋቂ ደራሲ እና ገጣሚ ሰዓሊ እና ምንትሶች ጋር ተዋውቂያለሁ። የብዙዎቹ መጽሐፎች አሉኝ፡፡ አብሮ ሻይ ቡና ማለቱ ከተራው ሕይወት ትንሽ ከፍ የማለት ስሜት አለው፤ አለ አይደል በቀጥታም ባይሆን “እንትናን አውቀዋለሁኮ!”… “ኧረ ባክሽ? ይኼ እንትን ፊልም የጻፈው? የእንትን መጽሐፍ ደራሲ" ...መባባል የሆነ ስሜት አለው፡፡ በተለይ ለእኔ ብዙ ነው ትርጉሙ፤ ሰው ከማያውቀው ሕመሜ ባይፈውሰኝም እንዳገግም ረድቶኛል፡፡ መልከ ጥፉ ነኝ፣ እራሴን ጠንቅቄ አውቃለሁ። መልኬ ወንዶችን አይስብም። ከእግሮቼና ከጥርሴ በስተቀር ምኔም ምኔም ዕይታ አይስብም፡፡ በእርግጥ ጓደኛዬ ማኅደረ ዓይኖችሽ ያምራሉ ትለኛለች፡፡ ሌላ ሰው ማንም ብሎኝ ስለማያውቅ እርግጠኛ አይደለሁም። ማኅደረ፣ ርግብ ነችና እባብም ቆንጆ ሆኖ የሚታያት ፍጥረት ነች፡፡ ለእሷ የሰው ልጅ በሙሉ ቆንጆ ነው፡፡ የኾነ ሆኖ አላምርምና ዕድሌ ነው ፤ ዓለም የቆንጆዎች ናት ብዬ ቁጭ ልል አልችልም፡፡ እዚሀ አስቀያሚ ሌጣ ደረቴ ውስጥ ያለው ልቤ ሥራው ደም መርጨት ብቻ አይደለምና እንደ ሰው የሚወደኝ የሚያፈቅረኝ ሰው እፈልጋለሁ። ሁልጊዜ ፍቅር እፈልጋለሁ፡፡ ዓይኖቼ ወንዶች ላይ እንደተንከራተቱ ናቸው፡፡ ግን ከ “ሃይስኩል” እስከ ኮሌጅ ፍቅረኛ ኖሮኝ አያውቅም። አደባባይ ላይ ተቁሞ ኡኡ... | የወንድ ያለኽ አይባል ነገር፡፡ ይኼ መገፋት ወደ ትምህርት ገፍቶኝ “ውይ እሷ እንደ
ወጣት አትልከሰከስ ትምህርቷ ላይ ብቻ...'' የሚባልልኝ ጎበዝ ተማሪ ሆንኩ፡፡ (ልልከስከስስ ብል...) ከዚያ በተረፈኝ ጊዜ ቤተክርስቲያን አዘወትራለሁ፡፡ ይኼም የጨዋነት ደረጃዬን ከፍ አደረገልኝ፡፡ የልቤን ናፍቆት ግን ማንም አያውቅም ነበር፡፡ እንዱ ይኼን ወረቀትሽን ወደዚያ ጣይና አግብቼ ልውሰድሽ ቢለኝ፣ ወደዚያ ወርውሬ እከተለው ነበር፡፡ በነጠላ የተሸፈነውም፣ በ'ሚንስከርት' ቡጊ ቡጊ የሚል ልቤ ነበር፡፡ ይገርመኛል ታዲያ፤ ከእህት በላይ የምታውቀኝ ጓደኛዬ ማኅደረን ጨምሮ የሚያውቁኝ ሁሉ የሚያስቡኝ ከዚህ በጣም አርቀው መሆኑ። እንዴት ዓይነት ማስመሰል ብከናነብ ነው? እላለሁ ለራሴ፡፡ ድፍን ወዳጅ ዘመዶቼ በአለፍ ገደም የሚያውቁኝ ሁሉ “ስለ ሃይሚ ጨዋነት በዐሥር ጣታችን እንፈርማለን!" ይላሉ። ከመፈረማችሁ በፊት ... በእርግጥ እንዲህ ስል ወንድ አላውቅም ማለቴ አልነበረም፡፡ አሳፋሪ ቢሆንም ወንድ ጋር መተኛት የጀመርኩት ገና የዐሥረኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ነው፡፡ ይኼንን ማንም አያውቅም ማኅደረን ጨምሮ።ምን ተብሎ ይነገራል!? የጎረቤታችን የእትዬ ሆህተ ባለቤት ጋሽ ዓለምነህ ጋር ተኛሁ ተብሎ? ለመጀመሪያ ጊዜ ወሲብ የፈጸምኩት እሱ ጋር ነበር፤ ረዥም ቀይ ነው፡፡ ለምን እንደሆነ እንጃ ሳዬው ዶክተር ነበር የሚመስለኝ፣ ኧረ ነጋዴ ነው ተብዬ ሁሉ ዶክተር ነበር የሚመስለኝ፡፡ አብረን እንድንተኛ ሲጠይቀኝ አልተግደረደርኩም(ጠዬቀኝ እንኳን አይባልም) እንዲያውም የሆነ ትልቅ ክብር ነበር የተሰማኝ። እትዬ ሆሀተ “እመብርሃንን የመሰለች" የሚባልላት ቆንጆ ሴት ነበረች፡፡ በፊልም የምናያቸውን የሀንድ ሴት ተዋናያን የመሰለች። በሙያዋ እዚህ ልደታ ፍርድ ቤት ዳኛ ነች፡፡ ሁሉም ሰው እትዬ ይላታል እንጂ፣ ያኔ ዕድሜዋ ከሰላሳ መብለጡን እንጃ፡፡ ታዲያ ባለቤቷ ጋሽ ዓለምነህን (ዓለምዬ ነዉ የምትለው) ከትምህርት ቤታችን ወረድ ብሎ የሕንፃ መሣሪያዎች መሸጫ መደብር ነበረው፣ ነጋዴ ነው፡፡ እኔና ማኅደረ ከትምህርት ቤት ወጥተን ወደ ቤታችን ስናዘግም ድንገት ከተገጣጠምን ያቺን ነጭ
ቶዮታ ኮሮላውን ያቆምና “ኑ! ግቡ'' ይለናል፡፡ እየተሸኮረመምን አንቺ ቅደሚ፣ አንቺ እየተባባልን እንገባለን፣ ይሸኜናል፡፡ ማኅደረን ሜክሲኮ ጫፍ ላይ ካወረዳት በኋላ፣ እኔ ጋር አንድ ሰፈር ስለሆንን እንቀጥላለን፡፡ ብዙ ብዙ የሚያስቅ ነገር እያወራኝ፤ ብዙ ብዙ የሚገባኝንና የማይገባኝን የሥራ ጉዳይ ምናምን እያወራኝ ...ልክ እንደ ጓደኛዉ፣ ውስጤ በጣም ነበር የሚወደው፡፡ እንደዚያም ሆኖ በኋላ መመልከቻ መስተዋቱ ደጋግሞ ዓይኑን ጣል እያደረገ ሲመለከት ብዙ ጊዜ ዓይኖቻችን ቢገጣጠሙም፤ ያው እንደሁሉም ወንድ ማኅደረን ለአጓጉል ነገር የፈለጋት ነበር የመሰለኝ፡፡ ዓይኔ ንቁ ነው። እንዲያውም ማኅደረን በኋላ “ምንድን ነው ባለትዳር አይደል እንዴ? ዐሥር ጊዜ ያፈጥብሻል"አልኳት፡፡ ደንገጥ ብላ “አፈጠጠ እንዴ?...አላዬሁትም'' አለች፡፡ ሁልጊዜ የሷን ወንዶች የማዬው እኔ ነኝ፡፡ እንዲህ ሲሆን ልለምደው ያልቻልኩት ብስጭት ውስጤ ይፈነዳል፡፡ ደንገጡር የሆንኩ ዓይነት። ማኅደረ ጋር የሚያገኙን ወንዶች ሁሉ ከመጀመሪያዋ ሰላምታ በኋላ ከነመፈጠሬ እንደረሱኝ ነው “የት ነው የምትማሩት? ...ስንተኛ ክፍል ናችሁ?...የት እየሄዳችሁ ነው? ..." የሚሉ ጥያቄዎች ሁሉ እኔን ማጀቢያ አድርገው ለማኅደረ የሚቀርቡ ነበሩ፡፡ ጥያቄያቼውን የምመልሰው እንደ አስተርጓሚ እኔ ነበርኩ፡፡ ማኅደረ ሲበዛ ዝምተኛ ናትና የእሷ አንደበት ነበርኩ፡፡ እኔ እየመለስኩ የእሷን ዓይን ለማዬት የሚታገሉት ነገር ያበሳጨኛል፤ምንም ልበል ግድ አልነበራቼውም “ራሴን ላጠፋ እየሄድኩ ነው'' ብላቼው ራሱ ግድ የሚሰጣቼው አይመስለኝም። ታዲያ አንድ ቀን ማኅደረ አባቷ ታመው፣ ከትምህርት ቤት ቀርታ ብቻዬን ታክሲ ስጠብቅ የጋሽ ዓለምነህን መኪና ከሰፈር ስትመጣ አዬኋት፡፡ ብቻዬን ስለሆንኩ እንዳላዬ ያልፈኛል ብዬ እኔም ያላዬሁት ለመምሰል እዚህና እዚያ ዓይኔን ሳቃብዝ፣ ያቺን መኪናውን ፊት ለፊቴ አቆመና መስተዋቱን ዝቅ አድርጎ “ሃይማኖት” ብሎ ጠራኝ፡፡ ታክሲ የሚጠብቀው ሰው ሁሉ ስሙ ሃይማኖት ይመስል ሁሉም ወደ እሱ
ዞረ። በእጁ ምልካት ወደ መኪናው እንድገባ ጠራኝ፣አባቴ ነበር የሚመስለው.. አላንገራገርኩም፣ የኋላውን በር ልከፍት ስታገል...ነይ እዚህ ብሎ ተንጠራርቶ የጋቢናውን በር ከፈተልኝ፡፡ ትንንሽ ነገሮች አሉ ምናልባት ለሌሎች ምንም የሆኑ፡፡ ለእኔ ግን ያች ቅጽበት የንግሥና ዙፋን ላይ የመቀመጥ ያኽል ልዩ የመከበር ስሜት ነበራት፡፡ ሁልጊዜ ይቺን የጋሽ ዓለምነህ ቶዮታ ኮሮላ መኪና ሰፈር ውስጥ በተለይ ማታ ላይ ሳያት፣ ሚስቱ እትዬ ሆህተ በክብር፣ ያኔ እኔ የተቀመጥኩበት ቦታ ላይ ተቀምጣ ነበር የማያት፡፡ ወደ ፊት የሚወደኝን ሰው አግብቼ እያልኩ የምመኜው ምኞት፣ በዚያ መስታወት አልፎ በዓይኔ የተፀነሰ ምቾት ነበር፡፡ በዚያ ላይ መኪናውን የሞላው ሽቶ...
👍37❤5
እስካሁን ያንን ቅጽበት ሳስብ ነፍሴ ሐሴት ታደርጋለች፡፡ የምድር ቆንጆ ሴቶች ሁሉ በእትዬ ሆሀተ ተወክለው የንግሥትነት ዙፋናቼውን የቀማኋቼው መስሎ ነው የሚሰማኝ። ሁልጊዜ ተሸናፊ ነኝ እንጂ፤ ነፍሴ ሽሚያና ውድድር ትወዳለች። ትንሽ እንደሄድን “ዓይናችን እያዬሽ አደግሽኮ ሃይሚ!?” አለኝ፡፡ ሃይሚ!? የምናገረው ጠፍቶኝ ዝም እንዳልኩ “ከማደግሽ፣ ቁንጅናሽ...! ስንተኛ ክፍል ሆንሽ?'' ብሎ እጁን...ያንን ንጹህ እና የሚያምር ቀኝ እጁን፣ ታፋዬ ላይ እንደ ቀልድ ጣል አደረገው፡፡ በድንገተኛው ንክኪ ስቅቅ አለኝ፣ እጁን ለመያዝ የላኩትን እጄን፣ በቀስታ ቀሚሴን ወደ ታች አስተካክዬ መለስኩት፤ግን ለመከላከል አልሞከርኩም። ዓይኖቼ ብቻ እጁ ላይ ተተከሉ፡፡ ትንሽ ዘወርወር _ አለብኝ፤ የመጀመሪያው አስተያዬት ከእጁ ጋር ተዳምሮ ስንተኛ ክፍል እንደሆንኩ ሁሉ እስኪጠፋብኝ ተደነባበርኩ፡፡ እጁ ወደ አጓጉል ቦታ ሲንቀሳቀስ ታፋና ታፋዬን በኃይል ገጥሜ፣ እጁን በእጄ ለማንሳት ያዝኩት “አይዞሽ ፈራሽ እንዴ?'' ብሎ እጁን ራሱ አነሳው፡፡ ከራሴ ክብር ይልቅ ያስቀዬምኩት ነበር የመሰለኝ “ይቅርታ ሰው ነክቶኝ ስለማያውቅ ነው'' አልኩት ፡፡ .“ግዴለም ... ያለ ነገር ነው ዕድሜሽ ነው፤ በዚያ ላይ ቆንጆ ሃሃሃሃሃ ..….እ….ስትወጭ እዚያ ፊት ለፊት ጁስ ቤቱ ጋ እጠብቅሻለሁ፣ አብረን እንሄዳለን" አለኝ፡ እንዳቀረቀርኩ “እሺ!” ብዬ ከመኪናው ወረድኩ። ዝብርቅርቅ እንዳለብኝ ትምሀርት
ቤት ውዬ ስወጣ በጉጉት ወደ ጁስ ቤቱ ተመለከትኩ መኪናዉ ቆማ ነበር።ልቤ እየደለቀች ግራና ቀኝ የሚያውቀኝ ሰው መኖር አለመኖሩን እያማተርኩ (እስኪ ምን አስፈራኝ) ወደ መኪናው ሄድኩ፡፡ በሩን ከውስጥ እየከፈተልኝ “ሃይሚ ቆንጆ ልጅ ...ግቢ ግቢ” አለኝ በፈገግታ ገብቼ ቁጭ አልኩ፡፡ ዐሥር ጊዜ አጭር የትምህርት ቤት ቀሚሴን ወደ ታች እየጎተትኩ እግሬን ለመሸፈን እሞክር ነበር፡፡ “እኔ የምልሽ ትንሽ ቆይተሺ ብትገቢ፣ ስመኝ ትጨነቅ ይሆን እንዴ?'' አለኝ፤ ስመጃ እናቴ ናት። ብዙ ጊዜ ቤተክርስቲያን ጉባኤ ካለ ከትምህርት ቤት ስወጣ በዛው ስለምሄድና አምሽቼ ስለምመለስ ምንም እንደማትል አውቃለሁ፡፡ “እዚያው ቤተስኪያኗ ሄዳ ነው" ከማለት ውጭ እናቴ ሌላ ቦታ ትሄዳለች ብላ ጠርጥራኝ አታውቅም፡፡ ግን ትንሽ መቆዬትን ምን አመጣዉ እያልኩ ምን እንደምመልስ በፍጥነት አስባለሁ ...አይሆንም ብል የሚቀረው ነገር ያጓጓኛል...ክፉኛ ጓጉቼ ነበር። እሺ ብልም ምን ይሆን የሚፈጠረው? የሚል ፍርኃት ያናውዘኛል፣ አፌ ላይ እንደመጣልኝ፣ “እኔ'ንጃ!'' አልኩ፡፡ ልምድ ያለው ሰውነውና ገብቶታል፣ ፈገግ ብሎ መኪናዋን ወደ ጦር ኃይሎች ያግለበልባት ጀመር፡፡ በዝምታ የሚያደርገውን አያለሁ። ጧት የመለሰውን እጁን እንደገና ወደ ታፋዬ ልኮ በቀስታ ቀሚሴን ወደ ላይ እንደመሰብሰብ ሲያደርገው በእጄ ያዝኩት “ሃይማኖት ..አሁን'ኮ ትልቅ፣ ቆንጆ፣ የደረሽ ልጅ ነሽ፤ አትፍሪ ...የከተማ ልጅ አይደለሽ እንዴ? በጣም ነው የወደድኩሽ” አለኝ፡፡ እጄን አላላሁ፤ እጁ ታፋዬ ላይ በቀስታ እየተንቀሳቀሰ የባጥ የቆጡን ያወራኛል፡፡ ምኑንም አልሰማውም፤ ወደ አንድ መኖሪያ ቤት ወደሚመስል ግቢ ገብቶ፣ መኪናውን አቆመና እንውረድ አለኝ፡፡
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
ቤት ውዬ ስወጣ በጉጉት ወደ ጁስ ቤቱ ተመለከትኩ መኪናዉ ቆማ ነበር።ልቤ እየደለቀች ግራና ቀኝ የሚያውቀኝ ሰው መኖር አለመኖሩን እያማተርኩ (እስኪ ምን አስፈራኝ) ወደ መኪናው ሄድኩ፡፡ በሩን ከውስጥ እየከፈተልኝ “ሃይሚ ቆንጆ ልጅ ...ግቢ ግቢ” አለኝ በፈገግታ ገብቼ ቁጭ አልኩ፡፡ ዐሥር ጊዜ አጭር የትምህርት ቤት ቀሚሴን ወደ ታች እየጎተትኩ እግሬን ለመሸፈን እሞክር ነበር፡፡ “እኔ የምልሽ ትንሽ ቆይተሺ ብትገቢ፣ ስመኝ ትጨነቅ ይሆን እንዴ?'' አለኝ፤ ስመጃ እናቴ ናት። ብዙ ጊዜ ቤተክርስቲያን ጉባኤ ካለ ከትምህርት ቤት ስወጣ በዛው ስለምሄድና አምሽቼ ስለምመለስ ምንም እንደማትል አውቃለሁ፡፡ “እዚያው ቤተስኪያኗ ሄዳ ነው" ከማለት ውጭ እናቴ ሌላ ቦታ ትሄዳለች ብላ ጠርጥራኝ አታውቅም፡፡ ግን ትንሽ መቆዬትን ምን አመጣዉ እያልኩ ምን እንደምመልስ በፍጥነት አስባለሁ ...አይሆንም ብል የሚቀረው ነገር ያጓጓኛል...ክፉኛ ጓጉቼ ነበር። እሺ ብልም ምን ይሆን የሚፈጠረው? የሚል ፍርኃት ያናውዘኛል፣ አፌ ላይ እንደመጣልኝ፣ “እኔ'ንጃ!'' አልኩ፡፡ ልምድ ያለው ሰውነውና ገብቶታል፣ ፈገግ ብሎ መኪናዋን ወደ ጦር ኃይሎች ያግለበልባት ጀመር፡፡ በዝምታ የሚያደርገውን አያለሁ። ጧት የመለሰውን እጁን እንደገና ወደ ታፋዬ ልኮ በቀስታ ቀሚሴን ወደ ላይ እንደመሰብሰብ ሲያደርገው በእጄ ያዝኩት “ሃይማኖት ..አሁን'ኮ ትልቅ፣ ቆንጆ፣ የደረሽ ልጅ ነሽ፤ አትፍሪ ...የከተማ ልጅ አይደለሽ እንዴ? በጣም ነው የወደድኩሽ” አለኝ፡፡ እጄን አላላሁ፤ እጁ ታፋዬ ላይ በቀስታ እየተንቀሳቀሰ የባጥ የቆጡን ያወራኛል፡፡ ምኑንም አልሰማውም፤ ወደ አንድ መኖሪያ ቤት ወደሚመስል ግቢ ገብቶ፣ መኪናውን አቆመና እንውረድ አለኝ፡፡
ይቀጥላል...
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
👍45
ሰው የሚማረው፣
አንድም ከፊደል፣
አንድም ከመከራ ነው፤
አንድ ቃል ከፊደል ጥበብ፣
አንድ ቃል ከመከራ መዝገብ፣
አንድም በሳር "ሀ" ብሎ፣
አንድም በአሣር "ዋ" ብሎ፤
🎴ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
አንድም ከፊደል፣
አንድም ከመከራ ነው፤
አንድ ቃል ከፊደል ጥበብ፣
አንድ ቃል ከመከራ መዝገብ፣
አንድም በሳር "ሀ" ብሎ፣
አንድም በአሣር "ዋ" ብሎ፤
🎴ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍21❤4
#የማይቻል_አንድ ነገር
እዉነት - ቤት ስትሰራ
ዉሸት - ላግዝ ካለች፣
ምስማር ካቀበለች፣
"ቤቱም አልተሰራ
እዉነትም አልኖረች።
🎴ጌትነት እንየው🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
እዉነት - ቤት ስትሰራ
ዉሸት - ላግዝ ካለች፣
ምስማር ካቀበለች፣
"ቤቱም አልተሰራ
እዉነትም አልኖረች።
🎴ጌትነት እንየው🎴
ቤተሰቦች #subscribe እያደረጋቹ
300 #Subscriber_Challenge
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍14👏4
እባክሽ አትሂጂ…..
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-14
///
ሰው ለጥቅሙ ሲል ነው የወደደኝ ብለህ አትማረር፡፡ እኛም እኮ ፀሀይን የምንወዳትና የምናፈቅራት ለሙቀቷ እና ለብርሀኗ ስንል ነው፤ለጥቅማችን ብለን..ከለበለዚያ እሰከመፈጠሯም ትዝ ላትለን ትችል ነበር፡፡ለጥቅም ሲባል መጥላትና መጉደት እንጂ ለጥቅም ሲሉ ማፍቀር ምን ክፍታ አለው፡፡
በሶስተኛው ቀን እራሴ በጥዋት እቤት ድረስ ሄድኩና በራሴ መኪና ልዕልትን ከነህመምተኛ ባለቤቷ ጭኜ ወደጓደኛዬ ኪኒሊክ ሄድን…ከጓደኛዬ ጋር ቀድሜ ተነጋግሬና ሁሉ ነገር አመቻችቼ ስለነበር ቀጥታ እንደደረስን ያለምንም ውጣ ውረድ በህመምተኛ ተሸክርካሪ አልጋ ላይ ተኝቶ በነርሶች እየተገፋ ማሽኑ ወደሚገኝበት ክፍል ሲወሰድ እኔና ልዕልት በረንዳ ላይ በሚገኝ ወንበር ላይ ጎን ለጎን ተቀምጠን መጠበቅ ጀመርን፡፡ይሄ ምርመራ ምንም ነገር እንደማይፈይድለትና ..እስከአሁን ስለመስፍን በሽታ ከምናውቀው ዝርዝር መረጃ ተጨማሪ እንደማያሳውቀን በእርግጠኝነት አውቃለሁ፡፡.ግን ይሄንን ምርመራ እንዲያደርግ የፈለኩት ከወንድሟ አቤል ጋር የተነጋርነውን ነገር ለማድረግ ሀሳቡን ለልዕልት ለማቅረብ እንዲያግዘኝና መነሻ ሰበበ ምክንት እንዲሆነኝ ብቻ ስለፈለኩ ነው፡፡በአንድ ሰዓት ሁሉ ነገር ተጠናቀቀና ..ውጤቱን በማግስቱ መጥተን እንድንወስድ ተነገሮን በሽተኛውን ተረከብን፡፡ጭኜ እንዳመጣኋቸው መልሼ ጭኜ ወደቤት ወሰደኳቸውና ጎን ለጎን ተሸክመን መልሰን መደበኛ አልጋው ላይ አስተኛነው..ጎን ለጎን ሆነን ከመኪናው አውርደን ስንሸከመው አንደኛው እጄና እጇን አንድ ላይ አቆላልፈን በሌለኛው እጃችን ትከሻውን ደግፈን ስለነበረ..ልቤን የሚያቀልጥ ጥልቅ ሙቀት ነበር የለቀቀችብኝ…የእሷን እጅ የጨበጠው እጄ ለዘላለም ባለበት ሆኖ ቢቀጥል ምኞቴ ነበር….የተሸከምነው ባለቤቷ እንኳን የህፃን ልጅ ያህል ስላልከበደኝ ምን አለw መኪናውም ቀርቶ ከሆስፒታል ጀምሮ እንደዚህ እጅ ለእጅ እንዳቆላለፍን ተሸክመነው በመጣን ኖር የሚል የጅል ምኞት በውስጤ በመብቀሉ ሳልፈልግ ፈገግ ለማለት ተገድጄ ነበር፡፡
‹‹በይ ልሄድ…ነገ ውጤቱን ተቀብዬ አመጣለሁ፡፡ ››
‹‹እንዴ ዶክተር..የምሳ ሰዓት ደርሷል ..ቁጭ በልና ምሳ በልተህ ትሄዳለህ›› ተላማጠቺኝ፡፡
‹‹አይ ቸኩላለሁ…በፍጥነት ወደሆስፒታል መመለስ አለብኝ..እዛው ቀለል ያለ ነገር እበላለሁ፡፡››
‹‹በጣም አስቸገርኩህ አይደል….ቆያ ጠብቀኝ ብሩን ይዤልህ ልምጣ››
ደነገጥኩ …‹‹የምኑን ብር?››
‹‹ለህክምና የከፈልከውን ነዋ…እርግጥ መጠኑን ስላላወቅኩ አሁን በርሳዬ ውስጥ ያለው ሀያ ሺ ብር ብቻ ነው….የጎደለውን ነገ አሞላላሁ፡፡››
‹‹የሄድንበት ኪኒኒክ የጓደኛዬ ነው ብዬሽ ነበር…. አዲስ ማሽን ስላስገባ እንደማስመረቂያ በነፃ ነው የሰራልኝ፡፡››
‹በፍፅም ዶ/ር..እንዲህ አይት ነገር ልቀበል አልችልም…ጠብቀኝ..››ተንደርድራ ወደ መኝታ ቤቷ ገባች፡፡ተንደርሬ ሳሎኑን ለቅቄ ወጣሁ፡፡ የውጩን በራፍ ከፈትኩና መኪናዬን ውስጥ ገብቼ ተፈተለኩ… ልትደርስብኝ ስትንደረደር አላቆምኩላትም፡፡ከሰፈር ራቅ እንዳልኩ ያቺ ዘወትር ለልዕልት መስጠት ያቃተኝን አበባ ሀምሳ ብር እየተቀበለች የምትቀበለኝ እብድ ቦታዋ ላይ ቁጭ ብላ መሬቱን ስትቆረቆር አገኘኋትና እንደወትሮዬ የአስፓቱን ጠርዝ ይዤ…..በዝግታ እየነዳው ስሮ ስደርስ አቆምኩ፡፡
‹‹እሼ እንዴት ነሽ?››
ቀና ብላ እንኳን ሳታየኝ‹‹50 ብር ካልከፈልከኝ..አበባውን አልቀበልህም፡፡ ››አለችኝ፡፡
ፈገግ አልኩ፡፡ኪሴ ገባሁና 50 ብር በማውጣት ሰጠኋት›ቀና አለችና በቆሻሻ የጠቋቆረ እጇን ዘረጋጀችና 50 ብሩን እየተቀበለቺኝ‹‹ ጎበዝ.. አሁን ደግሞ አበባውን አምጣ..››
‹‹ዛሬ አበባው የለም››
ክው ብላ ደነገጠች…በመደንገጧ እኔም አብሬያት ደነገጥኩ‹‹ምነው ..እሺ ብላ ተቀበለችህ እንዴ?››
‹‹አይ ዛሬ እረስቼው ….ባዶ እጄን ነወ የሄድኩት››
‹‹ወንዶች ድሮውንም ስልቹዎች ናቸሁ…ቶሎ ተስፋ ትቆርጣላችሁ….እሼ ዛሬ አበባውን ለመቀበል ዝግጁ የሆነችበት ቀን ቢሆንስ? ከሰርክ ማለት አይደል…?ለማንኛውም እንካ ››ብላ 50 ብሩን ወደእኔ ዘረጋች፡፡
‹‹ምን ላድርገው..ሰጠውሽ እኮ…ያንቺው ነው››
‹‹አይ..እኔ በነፃ ብር መቀበል አልወድም….በተለይ ከወንዶች የብላሽ ብር መቀበል መዘዙ ብዙ ነው››
ይህቺ ልጅ እብድ ነች ፋላስፋ አልኩና እጃን እንዳንከረፈፈች መኪናውን አስፈንጥሬ ጉዞዬን ቀጠልኩ….፡፡
በማግስቱ ደወልኩና ትናንት የተገናኘንበት ቦታ ቀጠርኳት..እያለከለከች መጣች።
ከሰላምታ በኃላ ቀጥታ ወደ ጥያቄ ነው የገባችም።
‹‹ዶ/ር ውጤቱ እንዴት ነው...?የተለየ ነገር አለው?››
‹‹ብዙም አይደል ...ብቻ?››
‹‹ብቻ ምን?››
‹‹ጓደኛዬ ማለት ምርመራውን ያደረግንበት ኪሊኒክ ባለቤት ከእኔ የተለየ እምነት ነው ያለው?››
‹‹ማለት ?››
‹‹እሱ ውጭ ሄዶ ቢታከም ቢያንስ የመዳን እድሉን አሁን ካለበት በ10 ፐርሰንት ይጨምራል የሚል ነው።››
‹‹አሪፍ ነዎ...አንተስ ዶ/ር ?በእሱ አስተያየት ላይ ሀሳብህ እንዴት ነው?››በመንሰፍሰፍ ጠየቀችኝ፡፡
‹‹እሱ እንዳለው ትንሽም ቢሆን የመዳን ቻንሱን በጥቂት ፐርሰንትም ቢሆን ሊጨምር ይችል ይሆናል ..ግን አቅሙ ይኖርሻል ወይ?ከዛ በኃላስ ካልተሳካስ?እሱ ነው የሚያሳስበኝ፡፡››
በአጠቃላይ ወሸት መጥፎና አሳፋሪ ነገር ነው፡፡መሀላ በገቡለት በሞያ ሽፋን መዋሸት ግን የስብእና መቆሸሽን ያሳያል፡፡እራሴን ጠላሁት፡፡ምን እየሰራሁ ነው?
እሷ ቀጠለች"እንዴ ዶ/ር አንድ ፐርሰንት ተጨማሪ እድል የሚያስገኝለት ከሆነ ከመሞከር ወደኃላ አልልም...አቅሙ ላልከው የግድ ነው እንደምንም እሞክራለሁ?ካልሆነ ቤቴን አስይዤ ከባንክ እበደራለሁ ወይም ሙሉ በሙሉ ሸጠውና አነስ ያለ ማረፊያ ገዝቼ በተቀረው አሳክመዎለሁ..."
‹‹ቁርጠኝነቷን ሳይ ፋዝዝ ብዬ በትኩረት አጤናት ጀመር››
‹‹ይሄውልሽ ልዕልት ..ቀስ ብለሽ ተረጋግተሽ ከዘመድም ከወዳጅም ጋር ምከሪበት...ከዛ መልሰን እናወራበትና ››
‹‹አይ ወስኜለሁ..በዚህ ጉዳይ ከማንም ጋር መደራደር አልፈልግም…የሚያግዘኝ ከላ ከጎኔ ይሰለፍ…አሻረኝ የሚል ሰው ደግሞ ከመንገዴ ገለል ይበል ››ብላ ተሰናብታኝ ወደ ቤቷ ተመለሰች፡፡የሆነውን ለወንድሞ ደውዬ ነገርኩት፡፡በደስታ ፈነጠዘና ረጅም ምስጋና አዥጎደጎደልኝ፡፡
///
ፍቅር ማለት …ሁለት ልቦች በአንድ ቅኝት አንድ አይነት የልብ-ምት ሲያሰሙ ማለት ነው….፡፡፡ግን እኔና ልእልት እኮ በአንድ አይነት ቅኝት አንድ አይነት የልብ ምት እያስደመጥን አይደለም፡፡የእኔ ልብ ለእሷ ሲንዷዷ…የእሷ ልብ ደግሞ ለመስፍን ይንዷቆዶቃል፡፡የእሱስ ልብ ለማን ይሆን የሚመታው..አሁንም ለብዙ ሴቶች በአንድ ጊዜ ይመታ ይሆን ወይስ ፍቅር የሚባለውን ነገር አለም ረስቶ በህይወት ስለመቆየት ብቻ እያሰበ ይሆን…?
ሚስቶቻችንን እንዳፈቀርናቸው እስከመጨረሻ መዝለቅ አንችልም..ጥቂት አመት አብረን ከኖርን እናቶቻቸን ይሆናሉ።አብዛኛዎቹ የተሳካላቸው ሚስቶች ባለቤቷን እንደመጀመሪያ ልጇ ነው የምታየው... የምትንከባከበውም።ልክ አሁን ልዕልተ መስፍን ለተባለው ባሏ እንደምታደርገው ማለት ነው፡፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-14
///
ሰው ለጥቅሙ ሲል ነው የወደደኝ ብለህ አትማረር፡፡ እኛም እኮ ፀሀይን የምንወዳትና የምናፈቅራት ለሙቀቷ እና ለብርሀኗ ስንል ነው፤ለጥቅማችን ብለን..ከለበለዚያ እሰከመፈጠሯም ትዝ ላትለን ትችል ነበር፡፡ለጥቅም ሲባል መጥላትና መጉደት እንጂ ለጥቅም ሲሉ ማፍቀር ምን ክፍታ አለው፡፡
በሶስተኛው ቀን እራሴ በጥዋት እቤት ድረስ ሄድኩና በራሴ መኪና ልዕልትን ከነህመምተኛ ባለቤቷ ጭኜ ወደጓደኛዬ ኪኒሊክ ሄድን…ከጓደኛዬ ጋር ቀድሜ ተነጋግሬና ሁሉ ነገር አመቻችቼ ስለነበር ቀጥታ እንደደረስን ያለምንም ውጣ ውረድ በህመምተኛ ተሸክርካሪ አልጋ ላይ ተኝቶ በነርሶች እየተገፋ ማሽኑ ወደሚገኝበት ክፍል ሲወሰድ እኔና ልዕልት በረንዳ ላይ በሚገኝ ወንበር ላይ ጎን ለጎን ተቀምጠን መጠበቅ ጀመርን፡፡ይሄ ምርመራ ምንም ነገር እንደማይፈይድለትና ..እስከአሁን ስለመስፍን በሽታ ከምናውቀው ዝርዝር መረጃ ተጨማሪ እንደማያሳውቀን በእርግጠኝነት አውቃለሁ፡፡.ግን ይሄንን ምርመራ እንዲያደርግ የፈለኩት ከወንድሟ አቤል ጋር የተነጋርነውን ነገር ለማድረግ ሀሳቡን ለልዕልት ለማቅረብ እንዲያግዘኝና መነሻ ሰበበ ምክንት እንዲሆነኝ ብቻ ስለፈለኩ ነው፡፡በአንድ ሰዓት ሁሉ ነገር ተጠናቀቀና ..ውጤቱን በማግስቱ መጥተን እንድንወስድ ተነገሮን በሽተኛውን ተረከብን፡፡ጭኜ እንዳመጣኋቸው መልሼ ጭኜ ወደቤት ወሰደኳቸውና ጎን ለጎን ተሸክመን መልሰን መደበኛ አልጋው ላይ አስተኛነው..ጎን ለጎን ሆነን ከመኪናው አውርደን ስንሸከመው አንደኛው እጄና እጇን አንድ ላይ አቆላልፈን በሌለኛው እጃችን ትከሻውን ደግፈን ስለነበረ..ልቤን የሚያቀልጥ ጥልቅ ሙቀት ነበር የለቀቀችብኝ…የእሷን እጅ የጨበጠው እጄ ለዘላለም ባለበት ሆኖ ቢቀጥል ምኞቴ ነበር….የተሸከምነው ባለቤቷ እንኳን የህፃን ልጅ ያህል ስላልከበደኝ ምን አለw መኪናውም ቀርቶ ከሆስፒታል ጀምሮ እንደዚህ እጅ ለእጅ እንዳቆላለፍን ተሸክመነው በመጣን ኖር የሚል የጅል ምኞት በውስጤ በመብቀሉ ሳልፈልግ ፈገግ ለማለት ተገድጄ ነበር፡፡
‹‹በይ ልሄድ…ነገ ውጤቱን ተቀብዬ አመጣለሁ፡፡ ››
‹‹እንዴ ዶክተር..የምሳ ሰዓት ደርሷል ..ቁጭ በልና ምሳ በልተህ ትሄዳለህ›› ተላማጠቺኝ፡፡
‹‹አይ ቸኩላለሁ…በፍጥነት ወደሆስፒታል መመለስ አለብኝ..እዛው ቀለል ያለ ነገር እበላለሁ፡፡››
‹‹በጣም አስቸገርኩህ አይደል….ቆያ ጠብቀኝ ብሩን ይዤልህ ልምጣ››
ደነገጥኩ …‹‹የምኑን ብር?››
‹‹ለህክምና የከፈልከውን ነዋ…እርግጥ መጠኑን ስላላወቅኩ አሁን በርሳዬ ውስጥ ያለው ሀያ ሺ ብር ብቻ ነው….የጎደለውን ነገ አሞላላሁ፡፡››
‹‹የሄድንበት ኪኒኒክ የጓደኛዬ ነው ብዬሽ ነበር…. አዲስ ማሽን ስላስገባ እንደማስመረቂያ በነፃ ነው የሰራልኝ፡፡››
‹በፍፅም ዶ/ር..እንዲህ አይት ነገር ልቀበል አልችልም…ጠብቀኝ..››ተንደርድራ ወደ መኝታ ቤቷ ገባች፡፡ተንደርሬ ሳሎኑን ለቅቄ ወጣሁ፡፡ የውጩን በራፍ ከፈትኩና መኪናዬን ውስጥ ገብቼ ተፈተለኩ… ልትደርስብኝ ስትንደረደር አላቆምኩላትም፡፡ከሰፈር ራቅ እንዳልኩ ያቺ ዘወትር ለልዕልት መስጠት ያቃተኝን አበባ ሀምሳ ብር እየተቀበለች የምትቀበለኝ እብድ ቦታዋ ላይ ቁጭ ብላ መሬቱን ስትቆረቆር አገኘኋትና እንደወትሮዬ የአስፓቱን ጠርዝ ይዤ…..በዝግታ እየነዳው ስሮ ስደርስ አቆምኩ፡፡
‹‹እሼ እንዴት ነሽ?››
ቀና ብላ እንኳን ሳታየኝ‹‹50 ብር ካልከፈልከኝ..አበባውን አልቀበልህም፡፡ ››አለችኝ፡፡
ፈገግ አልኩ፡፡ኪሴ ገባሁና 50 ብር በማውጣት ሰጠኋት›ቀና አለችና በቆሻሻ የጠቋቆረ እጇን ዘረጋጀችና 50 ብሩን እየተቀበለቺኝ‹‹ ጎበዝ.. አሁን ደግሞ አበባውን አምጣ..››
‹‹ዛሬ አበባው የለም››
ክው ብላ ደነገጠች…በመደንገጧ እኔም አብሬያት ደነገጥኩ‹‹ምነው ..እሺ ብላ ተቀበለችህ እንዴ?››
‹‹አይ ዛሬ እረስቼው ….ባዶ እጄን ነወ የሄድኩት››
‹‹ወንዶች ድሮውንም ስልቹዎች ናቸሁ…ቶሎ ተስፋ ትቆርጣላችሁ….እሼ ዛሬ አበባውን ለመቀበል ዝግጁ የሆነችበት ቀን ቢሆንስ? ከሰርክ ማለት አይደል…?ለማንኛውም እንካ ››ብላ 50 ብሩን ወደእኔ ዘረጋች፡፡
‹‹ምን ላድርገው..ሰጠውሽ እኮ…ያንቺው ነው››
‹‹አይ..እኔ በነፃ ብር መቀበል አልወድም….በተለይ ከወንዶች የብላሽ ብር መቀበል መዘዙ ብዙ ነው››
ይህቺ ልጅ እብድ ነች ፋላስፋ አልኩና እጃን እንዳንከረፈፈች መኪናውን አስፈንጥሬ ጉዞዬን ቀጠልኩ….፡፡
በማግስቱ ደወልኩና ትናንት የተገናኘንበት ቦታ ቀጠርኳት..እያለከለከች መጣች።
ከሰላምታ በኃላ ቀጥታ ወደ ጥያቄ ነው የገባችም።
‹‹ዶ/ር ውጤቱ እንዴት ነው...?የተለየ ነገር አለው?››
‹‹ብዙም አይደል ...ብቻ?››
‹‹ብቻ ምን?››
‹‹ጓደኛዬ ማለት ምርመራውን ያደረግንበት ኪሊኒክ ባለቤት ከእኔ የተለየ እምነት ነው ያለው?››
‹‹ማለት ?››
‹‹እሱ ውጭ ሄዶ ቢታከም ቢያንስ የመዳን እድሉን አሁን ካለበት በ10 ፐርሰንት ይጨምራል የሚል ነው።››
‹‹አሪፍ ነዎ...አንተስ ዶ/ር ?በእሱ አስተያየት ላይ ሀሳብህ እንዴት ነው?››በመንሰፍሰፍ ጠየቀችኝ፡፡
‹‹እሱ እንዳለው ትንሽም ቢሆን የመዳን ቻንሱን በጥቂት ፐርሰንትም ቢሆን ሊጨምር ይችል ይሆናል ..ግን አቅሙ ይኖርሻል ወይ?ከዛ በኃላስ ካልተሳካስ?እሱ ነው የሚያሳስበኝ፡፡››
በአጠቃላይ ወሸት መጥፎና አሳፋሪ ነገር ነው፡፡መሀላ በገቡለት በሞያ ሽፋን መዋሸት ግን የስብእና መቆሸሽን ያሳያል፡፡እራሴን ጠላሁት፡፡ምን እየሰራሁ ነው?
እሷ ቀጠለች"እንዴ ዶ/ር አንድ ፐርሰንት ተጨማሪ እድል የሚያስገኝለት ከሆነ ከመሞከር ወደኃላ አልልም...አቅሙ ላልከው የግድ ነው እንደምንም እሞክራለሁ?ካልሆነ ቤቴን አስይዤ ከባንክ እበደራለሁ ወይም ሙሉ በሙሉ ሸጠውና አነስ ያለ ማረፊያ ገዝቼ በተቀረው አሳክመዎለሁ..."
‹‹ቁርጠኝነቷን ሳይ ፋዝዝ ብዬ በትኩረት አጤናት ጀመር››
‹‹ይሄውልሽ ልዕልት ..ቀስ ብለሽ ተረጋግተሽ ከዘመድም ከወዳጅም ጋር ምከሪበት...ከዛ መልሰን እናወራበትና ››
‹‹አይ ወስኜለሁ..በዚህ ጉዳይ ከማንም ጋር መደራደር አልፈልግም…የሚያግዘኝ ከላ ከጎኔ ይሰለፍ…አሻረኝ የሚል ሰው ደግሞ ከመንገዴ ገለል ይበል ››ብላ ተሰናብታኝ ወደ ቤቷ ተመለሰች፡፡የሆነውን ለወንድሞ ደውዬ ነገርኩት፡፡በደስታ ፈነጠዘና ረጅም ምስጋና አዥጎደጎደልኝ፡፡
///
ፍቅር ማለት …ሁለት ልቦች በአንድ ቅኝት አንድ አይነት የልብ-ምት ሲያሰሙ ማለት ነው….፡፡፡ግን እኔና ልእልት እኮ በአንድ አይነት ቅኝት አንድ አይነት የልብ ምት እያስደመጥን አይደለም፡፡የእኔ ልብ ለእሷ ሲንዷዷ…የእሷ ልብ ደግሞ ለመስፍን ይንዷቆዶቃል፡፡የእሱስ ልብ ለማን ይሆን የሚመታው..አሁንም ለብዙ ሴቶች በአንድ ጊዜ ይመታ ይሆን ወይስ ፍቅር የሚባለውን ነገር አለም ረስቶ በህይወት ስለመቆየት ብቻ እያሰበ ይሆን…?
ሚስቶቻችንን እንዳፈቀርናቸው እስከመጨረሻ መዝለቅ አንችልም..ጥቂት አመት አብረን ከኖርን እናቶቻቸን ይሆናሉ።አብዛኛዎቹ የተሳካላቸው ሚስቶች ባለቤቷን እንደመጀመሪያ ልጇ ነው የምታየው... የምትንከባከበውም።ልክ አሁን ልዕልተ መስፍን ለተባለው ባሏ እንደምታደርገው ማለት ነው፡፡
👍48❤7
ምንም ምርጫ አልሰጠችኝም...እድሜ ለወንድሟ ቅርቃር ውስጥ ገብቼያለሁ።አሁን በቃ መሄድ የለበትም እዚሁ እናክመዋለን ብላትም አሻፈረኝ አለች።እሺ ሌላ ሰው ወይም ወንድሙ ይዛት ይሂድ ብትባልም እኔ እያለሁ እንዴት ተደርጎ?አለች። አይኔ እያየ ለእሬሳ የቀረበ ሰው ለማዳን የልጆቾን ማሳደጊያ የወደፊት ጥሪቷን ሰብስባ ለማጥፋት ከመወሰኗም በላይ ልጆቾን ለቤተሠቦቾ ትታ እኔን አውላላ ሜዳ ላይ ጥላኝ በበአድ ሀገር… በአድ የሆነ ፈተና ለመጋፈጥ ልትሄድ ነው?‹‹መጀመሪያ እንግዲያው ለመሄድ በቁርጠኝነት ከወሰንሽ እኔም ልከተልሽ›› ልላት አስቤ ነው።ቆይቼ በመረጋጋት ሳሰላስለው የሚሆን ሆኖ አላገኘሁትም...‹‹ስራዬን እንዴት አደርጋለሁ?ሰውን በተለይ እናቴን ምን ብዬ አሳምናታለሁ...?እሺ እንደምንም ቀባጥሬና ለፍልፌ እናቴን ማሳመን ብችል እንኳን እራሷን ልዕልትን ምን ብዬ ነው ባልሽን ለማስታመም ስራዬን እርግፍ አድርጌ ትቼ አንቺን ተከትዬ ልሂድ ልላት የምችለው?እራስን ሙሉ በሙሉ አጋልጦ ትዝብት ላይ ከመውደቅ በስተቀር እሷን አሳምኖ ይሁንታ ማስገኘት የሚችል ሀሳብ አይደለም...በዚህ የተነሳ አራት ቀን ሌት ያለማቋረጥ ጨጓራዬ እስኪቆስል ድረስ ካሰብኩ በኃላ አንድ አደገኛና አስጠሊታ ውሳኔ ወሰንኩ...አሁን ውሳኔዬን ተግባራዊ ለማድረግ ሙሉ ዝግጅቴን አጠናቅቄ ወደ እነ ልዕልት ቤት እየሄድኩ ነው።
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
ይቀጥላል...
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
👍32❤4
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ፅዮን እና ታዲዬስ እሁድ ከምሽቱ 12 ሰዓት ሀዋሳ ሴንትራል ሆቴል ቁጭ ብላው እሷ ለስላሳ እሱ ቢራ አዛው እየተጐነጩ ያዘዙትን መክሰስ በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡የምረቃ በዓሉ ካለፈ በኃላ በሣምንታቸው ዛሬ መገናኘታቸው ነው፡፡‹‹እሺ ፅዮን ለምን ግን ወይን ነገር አትሞክሪም ነበር?››
<<አንደኛ አልኮል የሚባል ነገር ሞክሬ አላውቅም ...ሁለተኛ የማያየው ዓይኔ ሳያንስ ጠጥቼ እምሮዬንም እንዳያይ አድርጌ እንዴት ልሆን ነው?››
‹‹አይ ሳታበዢ ማለቴ እኮ ነው፡፡››
‹‹ያው መጠጣት ከጀመርኩ ቢያንስ አንድ ብርጭቆ መጨረሴ ይቀራል..ያ ማለት ደግሞ እኔን ለማስከር በቂ መጠን ነው…ግድ የለህም ለስላሳው ይብቃኝ፡፡››
‹‹ያው ብትሰክሪም እኮ እኔ አብሬሽ አለሁ ብዬ ነው፡፡››
‹‹አይ እኔ በራሴ ድክመት እራሴን ጥዬ ሰውን ደግፉኝ ማለት አይመቸኝም፡፡››
‹‹ተቀብያለሁ››አለ በጠንካራ መንፈሷ ተደስቶባት፡፡
‹‹ፂ ስለበቀደሙ ጉዳይ እንድናወራ ነው ዛሬ የቀጠርኩሽ››ወደዋናው ቁምነገር ድንገት ገባ።
‹‹ይመቸኛል..እኔም እንደዛ እንደሆነ ተስፋ በማድረግ ነው የመጣሁት..ቀጥል፡፡››
‹‹እንዴት እንደምቀጥል አላውቅም፤ብቻ…..››
‹‹ታዲ ..እኔ የ28 ዓመት ወጣት ነኝ፤በህይወቴ ብዙ ውጣ ውረድ ያየው ሰው ነኝ.. ህይወት ነጩንም ሆነ ጥቁሩን ክፍሎቿን በማፈራረቅ አሳይታኛለች፡፡አንድን ነገር ፈልጌዋለሁና የግድ አገኘዋለሁ ማለት እንዳልሆነ አውቃለሁ፡፡››
‹‹በህይወትማ ምንም ነገር ከልብሽ አገኘዋለሁ ብለሽ ካሰብሽ ታገኚዋለሽ፡፡››
‹‹አውቃለሁ....የሆነ ነገር አገኛለሁ ብለህ ከልብህ ከተመኘህ፤ ምኞትህንም ለማሳካት በሙሉ ጉልበትህ ከተንቀሳቀስክ የማይሳካልህ ነገር እንደሌለ እኔም አምናለሁ፤ይሄ ግን ፍቅር ላይ ሲሆን ከሚሰራበት ጊዜ ይልቅ የማይሰራበት ጊዜ ይበልጣል፡፡››
‹‹እንዴት እንዲህ ልትይ ቻልሽ…?ከፍቅር አምላክ ጋር ትንሽ የተቀያየማችሁ ይመስላል፡፡››
‹‹ትንሽ አልከው...ምን ትንሽ ብቻ ...ለአምስት አመት ተኮራርፈን በደረሰበት ላልደርስ ተማምለን… ሳይደርስብኝ ሳልደርስበት ጥሩ ጊዜ አሳልፈን ነበር ፡፡››
‹‹ታዲያ እንዴት ሆናችሁ?››
‹‹ምን እንዴት ሆናችሁ አለው... አንተን ሳገኝ መሀላዬን አፍርሼ ደጅ እየፀናሁ እያየኸኝ?››
‹‹ደጅ ጽናት አልሽው፤ለማንኛውም እስኪ በምን ተኮራርፋችሁ እንደነበረ ብትነግሪኝ ? ማለት ደስ ካለሽ…..››
ዝም አለች... ጭንቅላቷ ወደታች ተደፋ‹‹…ምን መሰለህ......››ብላ ልትቀጥል ስትል ያዘዙት መክሰስ መጣና ቀረበላቸው፡እየተጎራረሱ በሉ..ከጨረሡ በኃላ አብረው ወደ እጅ መታጠቢያው በመሄድ ታጠቡና ወደመቀመጫቸው ተመለሱ፡፡ታዲዬስ ሁለተኛ ቢራውን አዘዘ..ዛሬ ካለወትሮው ጠጣ ጠጣ አሰኝቶታል፡፡
‹‹ምነው ዝም አልከኝ ...?››አለችው ልትጀምርለት የነበረውን ታሪኳን እንድትቀጥልለት ባለመጠየቁ ቅር ብሏት...
‹‹ኧረ ዝም አላልኩሽም ….ዝም ስላልሽ እኮ ዝምታሽን ላለመረበሽ ብዬ ነው፤እኔ ዝምታዬን ከሚረቡሹኝ ንግግሬን ቢያቋርጡኝ ይሻለኛል፡፡››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው….ግን አሁን ዝምታ ውስጥ ስላልሆንኩ አትረብሸኝም
...ይሄውልህ ታዲ እኔ የሻሸመኔ ልጅ ነኝ፡፡ ትውልዴ እስከተወሰነ ጊዜም እድገቴም እዛ ነው፡፡ አባቴን እና እናቴን አላውቃቸውም ማለቴ በአካል አላውቃቸውም...ያሳደገችኝ የአባቴ እናት አያቴ ነች ... እናቴ ገና አንድ አመት ሳይሞላኝ ነው አባቴ ክንድ ላይ ጥላኝ ሀገሩን ጥላ የጠፋችው፡፡ ከአንድ አመት በኃላ አባቴም በተራው ሁኔታዎች ስልችት ሲሉት እኔን ለእናቱ ሰጥቶኝ ውትድርና ተቀጥሮ ለጦርነት ወደ ሰሜን ይሄዳል፡፡
ከዛ በኃላ አያቴ ያለቻትን አንድ ክፍል ቤት በደባልነት አንድ ደደፎ ለሚባል ከገጠር ለትምህርት ለመጣ ልጅ አከራይታ ከእሱ ከምታገኘው ገቢ በተጨማሪም በደካማ አቅሟ ጠላ እየጠመቀች አንዳንዴም አረቄ እያወጣች በመሸጥ እኔን ማሳደግ ትጀምራለች ፡፡ስምንት ዓመት ሲሞላኝ ግን ያልታሰበ ችግር ተፈጠረ..
ዓይኖቼን ይጋርደኝ ጀመር ..በወቅቱ አያቴ እንኳን ለህክምና ለሆዴም መሙያ የሚሆን ሳንቲም ለማግኘት በመከራ ነበር ሚሳካላት…፡፡
ባቅሟ የቻለችውን ፀበሉንም የባህል መድሀኒቱንም ብትሞክርልኝም ከቀን ወደቀን እየባሰብኝ መጥቶ ከአንድ አመት በኃላ ሙሉ በሙሉ ሁለቱም አይኖቼ ታወሩ..ከዛ ትምህርቴንም ከሁለተኛ ክፍል ግማሽ ላይ አቆረጥኩ፡፡አያቴ ግራ ገባት ፡፡በሚመጣው አመት ግን ያ እቤታችን በደባልነት ይኖር የነበር ያልኩህ ተማሪው ልጅ ሚሽኖቹ ጋር ተሯሩጦ በአዳሪነት አስገባኝ፡፡ ይገርምሀል አያቴን ልክ እንደእናቱ ነበር የሚወዳት... እሷም ከእኔ ለይታ አታየውም ነበር እንዲሁ ስሙ ተከራይ ተባለ እንጂ እኛ የምንበላውን ይበላል እሱ የሚበላውን እንበላለን ስናጣ አብረን እንራባለን፡
እኔ ሚሽን በአዳሪነት ከገባሁ በኃላ አያቴ ጋር እኖር ከነበረው ኑሮ በተሻለ ሁኔታ እኖር ጀመር፤ ትምህርቴንም በጥሩ ሁኔታ መከታተል ጀመርኩ፤ድንገት ግን ምን እንደተፈጠረ ታውቃለህ? ብቸኛ ዘመዴ የሆነችው አያቴ ሞተች፡፡በወቅቱ የ5ተኛ ክፍል ተማሪ ነበርኩ… ዕድሜዬም ወደ 14 አካባቢ ተጠግቶ ነበር ..በጣም ነው የከበደኝ፡፡ ለመጽናናት በጣም አስቸግሬ ነበር፡፡ይገርምሀል እቤታችንን ተከራይቶ ነበር ያልኩህ ልጅ በወቅቱ አስረኛ ክፍል ደርሶ ነበር፡፡በአያቴን ሞት በጣም ነበር ያዘነው…፡፡
ከዛ እኔን መንከባከብ የእሱ ኃላፊነት እንደሆነ ነበር የሚያስበው፤ በሳምንት ሁለት ቀን እየመጣ ይጠይቀኝ ነበር፤ደግሞ ሲመጣ ባዶ እጁን አይመጣም..ደብተር፣እስኪሪብቶ፣የፀጉር ቅባት፣ማበጠሪያ፣ፓንት ...ብቻ የማይገዛልኝ ነገር አልነበረም፤ካጣ ካጣ የ 25 ሳንቲም ማስቲካም ቢሆን ይዞልኝ ይመጣል..ደግሞ እኮ የሚገርመው እሱም ምንም የሌለው የደሀ ገበሬ ልጅ መሆኑ ነው፡፡ ግማሽ ቀን ይማራል ኑሮውን ለመደጎም ደግሞ ግማሽ ቀን ጋራዥ ይሰራል...ከዛ በሚያገኛት ሽርፍራፊ ገንዘብ ነበር ለእኔ የሚያስፈልገኝን ነገር ይገዛልኝ የነበርው፡፡
በዛ ላይ የቤት ኪራዬን በየወሩ ቀን እንኳን ሳያስተጎጉል አምጥቶ ይሰጠኛል…ተወው ይቅር አያስፈልገኝም ብለውም አይሰማኝም...‹ነገ ብትቸገሪ ለአንድ ነገር ይሆንሻል.. አስቀምጪው >> ይለኛል...እኔ ደግሞ የተለየ ወጪ ስለሌለኝ እጄ ላይ እየተጠራቀመ ሲበዛብኝ አንድ የምወዳት አስተማሪዬ ጋር ማስቀመጥ ጀመርኩ፡፡
እንዲህ እንዲህ እያለ ቀናቶች እየነጐዱ እኔም እያደግኩ በትምህርቴም እየገፋሁ መጣሁ..በነገራችን ላይ ሙዚቃ መሳሪያ መነካካት የጀመርኩት እዛው ሻሸመኔ አይነስውራን ትምህርት ቤት እያለሁ ነበር፡፡
ስምንተኛ ክፍል ስደርስ ደደፎ 12ተኛ ክፍል ጨርሶ ነጥብ ስላልመጣለት መንጃ ፍቃድ አውጥቶ ሹፌር ሆነ፡፡በዚህን ጊዜ በሳምንት ሁለት ቀን መምጣቱን አቁሞ በሳምንት አንዴ
..አንዳንዴም በአስራአምስት ቀን አንዴ ይመጣ
ጀመር፡፡ሲመጣ ታዲያ ይዞልኝ የሚመጣውን
ነገር አትጠይቀኝ ... ምንም የሚቀረው ነገር
አልነበረም፤ለእኔ አይደለም ለጓደኞቼ እራሱ ይተርፍ ነበር፡፡ የጽዮን ወንድም መጣ ከተባለ ጓደኞቼ በሙሉ ጥርስ በጥርስ ነበር
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አራት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ፅዮን እና ታዲዬስ እሁድ ከምሽቱ 12 ሰዓት ሀዋሳ ሴንትራል ሆቴል ቁጭ ብላው እሷ ለስላሳ እሱ ቢራ አዛው እየተጐነጩ ያዘዙትን መክሰስ በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡የምረቃ በዓሉ ካለፈ በኃላ በሣምንታቸው ዛሬ መገናኘታቸው ነው፡፡‹‹እሺ ፅዮን ለምን ግን ወይን ነገር አትሞክሪም ነበር?››
<<አንደኛ አልኮል የሚባል ነገር ሞክሬ አላውቅም ...ሁለተኛ የማያየው ዓይኔ ሳያንስ ጠጥቼ እምሮዬንም እንዳያይ አድርጌ እንዴት ልሆን ነው?››
‹‹አይ ሳታበዢ ማለቴ እኮ ነው፡፡››
‹‹ያው መጠጣት ከጀመርኩ ቢያንስ አንድ ብርጭቆ መጨረሴ ይቀራል..ያ ማለት ደግሞ እኔን ለማስከር በቂ መጠን ነው…ግድ የለህም ለስላሳው ይብቃኝ፡፡››
‹‹ያው ብትሰክሪም እኮ እኔ አብሬሽ አለሁ ብዬ ነው፡፡››
‹‹አይ እኔ በራሴ ድክመት እራሴን ጥዬ ሰውን ደግፉኝ ማለት አይመቸኝም፡፡››
‹‹ተቀብያለሁ››አለ በጠንካራ መንፈሷ ተደስቶባት፡፡
‹‹ፂ ስለበቀደሙ ጉዳይ እንድናወራ ነው ዛሬ የቀጠርኩሽ››ወደዋናው ቁምነገር ድንገት ገባ።
‹‹ይመቸኛል..እኔም እንደዛ እንደሆነ ተስፋ በማድረግ ነው የመጣሁት..ቀጥል፡፡››
‹‹እንዴት እንደምቀጥል አላውቅም፤ብቻ…..››
‹‹ታዲ ..እኔ የ28 ዓመት ወጣት ነኝ፤በህይወቴ ብዙ ውጣ ውረድ ያየው ሰው ነኝ.. ህይወት ነጩንም ሆነ ጥቁሩን ክፍሎቿን በማፈራረቅ አሳይታኛለች፡፡አንድን ነገር ፈልጌዋለሁና የግድ አገኘዋለሁ ማለት እንዳልሆነ አውቃለሁ፡፡››
‹‹በህይወትማ ምንም ነገር ከልብሽ አገኘዋለሁ ብለሽ ካሰብሽ ታገኚዋለሽ፡፡››
‹‹አውቃለሁ....የሆነ ነገር አገኛለሁ ብለህ ከልብህ ከተመኘህ፤ ምኞትህንም ለማሳካት በሙሉ ጉልበትህ ከተንቀሳቀስክ የማይሳካልህ ነገር እንደሌለ እኔም አምናለሁ፤ይሄ ግን ፍቅር ላይ ሲሆን ከሚሰራበት ጊዜ ይልቅ የማይሰራበት ጊዜ ይበልጣል፡፡››
‹‹እንዴት እንዲህ ልትይ ቻልሽ…?ከፍቅር አምላክ ጋር ትንሽ የተቀያየማችሁ ይመስላል፡፡››
‹‹ትንሽ አልከው...ምን ትንሽ ብቻ ...ለአምስት አመት ተኮራርፈን በደረሰበት ላልደርስ ተማምለን… ሳይደርስብኝ ሳልደርስበት ጥሩ ጊዜ አሳልፈን ነበር ፡፡››
‹‹ታዲያ እንዴት ሆናችሁ?››
‹‹ምን እንዴት ሆናችሁ አለው... አንተን ሳገኝ መሀላዬን አፍርሼ ደጅ እየፀናሁ እያየኸኝ?››
‹‹ደጅ ጽናት አልሽው፤ለማንኛውም እስኪ በምን ተኮራርፋችሁ እንደነበረ ብትነግሪኝ ? ማለት ደስ ካለሽ…..››
ዝም አለች... ጭንቅላቷ ወደታች ተደፋ‹‹…ምን መሰለህ......››ብላ ልትቀጥል ስትል ያዘዙት መክሰስ መጣና ቀረበላቸው፡እየተጎራረሱ በሉ..ከጨረሡ በኃላ አብረው ወደ እጅ መታጠቢያው በመሄድ ታጠቡና ወደመቀመጫቸው ተመለሱ፡፡ታዲዬስ ሁለተኛ ቢራውን አዘዘ..ዛሬ ካለወትሮው ጠጣ ጠጣ አሰኝቶታል፡፡
‹‹ምነው ዝም አልከኝ ...?››አለችው ልትጀምርለት የነበረውን ታሪኳን እንድትቀጥልለት ባለመጠየቁ ቅር ብሏት...
‹‹ኧረ ዝም አላልኩሽም ….ዝም ስላልሽ እኮ ዝምታሽን ላለመረበሽ ብዬ ነው፤እኔ ዝምታዬን ከሚረቡሹኝ ንግግሬን ቢያቋርጡኝ ይሻለኛል፡፡››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው….ግን አሁን ዝምታ ውስጥ ስላልሆንኩ አትረብሸኝም
...ይሄውልህ ታዲ እኔ የሻሸመኔ ልጅ ነኝ፡፡ ትውልዴ እስከተወሰነ ጊዜም እድገቴም እዛ ነው፡፡ አባቴን እና እናቴን አላውቃቸውም ማለቴ በአካል አላውቃቸውም...ያሳደገችኝ የአባቴ እናት አያቴ ነች ... እናቴ ገና አንድ አመት ሳይሞላኝ ነው አባቴ ክንድ ላይ ጥላኝ ሀገሩን ጥላ የጠፋችው፡፡ ከአንድ አመት በኃላ አባቴም በተራው ሁኔታዎች ስልችት ሲሉት እኔን ለእናቱ ሰጥቶኝ ውትድርና ተቀጥሮ ለጦርነት ወደ ሰሜን ይሄዳል፡፡
ከዛ በኃላ አያቴ ያለቻትን አንድ ክፍል ቤት በደባልነት አንድ ደደፎ ለሚባል ከገጠር ለትምህርት ለመጣ ልጅ አከራይታ ከእሱ ከምታገኘው ገቢ በተጨማሪም በደካማ አቅሟ ጠላ እየጠመቀች አንዳንዴም አረቄ እያወጣች በመሸጥ እኔን ማሳደግ ትጀምራለች ፡፡ስምንት ዓመት ሲሞላኝ ግን ያልታሰበ ችግር ተፈጠረ..
ዓይኖቼን ይጋርደኝ ጀመር ..በወቅቱ አያቴ እንኳን ለህክምና ለሆዴም መሙያ የሚሆን ሳንቲም ለማግኘት በመከራ ነበር ሚሳካላት…፡፡
ባቅሟ የቻለችውን ፀበሉንም የባህል መድሀኒቱንም ብትሞክርልኝም ከቀን ወደቀን እየባሰብኝ መጥቶ ከአንድ አመት በኃላ ሙሉ በሙሉ ሁለቱም አይኖቼ ታወሩ..ከዛ ትምህርቴንም ከሁለተኛ ክፍል ግማሽ ላይ አቆረጥኩ፡፡አያቴ ግራ ገባት ፡፡በሚመጣው አመት ግን ያ እቤታችን በደባልነት ይኖር የነበር ያልኩህ ተማሪው ልጅ ሚሽኖቹ ጋር ተሯሩጦ በአዳሪነት አስገባኝ፡፡ ይገርምሀል አያቴን ልክ እንደእናቱ ነበር የሚወዳት... እሷም ከእኔ ለይታ አታየውም ነበር እንዲሁ ስሙ ተከራይ ተባለ እንጂ እኛ የምንበላውን ይበላል እሱ የሚበላውን እንበላለን ስናጣ አብረን እንራባለን፡
እኔ ሚሽን በአዳሪነት ከገባሁ በኃላ አያቴ ጋር እኖር ከነበረው ኑሮ በተሻለ ሁኔታ እኖር ጀመር፤ ትምህርቴንም በጥሩ ሁኔታ መከታተል ጀመርኩ፤ድንገት ግን ምን እንደተፈጠረ ታውቃለህ? ብቸኛ ዘመዴ የሆነችው አያቴ ሞተች፡፡በወቅቱ የ5ተኛ ክፍል ተማሪ ነበርኩ… ዕድሜዬም ወደ 14 አካባቢ ተጠግቶ ነበር ..በጣም ነው የከበደኝ፡፡ ለመጽናናት በጣም አስቸግሬ ነበር፡፡ይገርምሀል እቤታችንን ተከራይቶ ነበር ያልኩህ ልጅ በወቅቱ አስረኛ ክፍል ደርሶ ነበር፡፡በአያቴን ሞት በጣም ነበር ያዘነው…፡፡
ከዛ እኔን መንከባከብ የእሱ ኃላፊነት እንደሆነ ነበር የሚያስበው፤ በሳምንት ሁለት ቀን እየመጣ ይጠይቀኝ ነበር፤ደግሞ ሲመጣ ባዶ እጁን አይመጣም..ደብተር፣እስኪሪብቶ፣የፀጉር ቅባት፣ማበጠሪያ፣ፓንት ...ብቻ የማይገዛልኝ ነገር አልነበረም፤ካጣ ካጣ የ 25 ሳንቲም ማስቲካም ቢሆን ይዞልኝ ይመጣል..ደግሞ እኮ የሚገርመው እሱም ምንም የሌለው የደሀ ገበሬ ልጅ መሆኑ ነው፡፡ ግማሽ ቀን ይማራል ኑሮውን ለመደጎም ደግሞ ግማሽ ቀን ጋራዥ ይሰራል...ከዛ በሚያገኛት ሽርፍራፊ ገንዘብ ነበር ለእኔ የሚያስፈልገኝን ነገር ይገዛልኝ የነበርው፡፡
በዛ ላይ የቤት ኪራዬን በየወሩ ቀን እንኳን ሳያስተጎጉል አምጥቶ ይሰጠኛል…ተወው ይቅር አያስፈልገኝም ብለውም አይሰማኝም...‹ነገ ብትቸገሪ ለአንድ ነገር ይሆንሻል.. አስቀምጪው >> ይለኛል...እኔ ደግሞ የተለየ ወጪ ስለሌለኝ እጄ ላይ እየተጠራቀመ ሲበዛብኝ አንድ የምወዳት አስተማሪዬ ጋር ማስቀመጥ ጀመርኩ፡፡
እንዲህ እንዲህ እያለ ቀናቶች እየነጐዱ እኔም እያደግኩ በትምህርቴም እየገፋሁ መጣሁ..በነገራችን ላይ ሙዚቃ መሳሪያ መነካካት የጀመርኩት እዛው ሻሸመኔ አይነስውራን ትምህርት ቤት እያለሁ ነበር፡፡
ስምንተኛ ክፍል ስደርስ ደደፎ 12ተኛ ክፍል ጨርሶ ነጥብ ስላልመጣለት መንጃ ፍቃድ አውጥቶ ሹፌር ሆነ፡፡በዚህን ጊዜ በሳምንት ሁለት ቀን መምጣቱን አቁሞ በሳምንት አንዴ
..አንዳንዴም በአስራአምስት ቀን አንዴ ይመጣ
ጀመር፡፡ሲመጣ ታዲያ ይዞልኝ የሚመጣውን
ነገር አትጠይቀኝ ... ምንም የሚቀረው ነገር
አልነበረም፤ለእኔ አይደለም ለጓደኞቼ እራሱ ይተርፍ ነበር፡፡ የጽዮን ወንድም መጣ ከተባለ ጓደኞቼ በሙሉ ጥርስ በጥርስ ነበር
👍73❤8
የሚሆኑት...ታዲያ በዛን ወቅት እሱ ሄዶ መልሶ
እስኪመጣ ድረስ ክፉኛ በናፍቆት እሰቃይ
ጀመር፡፡ ሳይደበዝዝ በውስጤ ተቀርጾ የቀረው
የእሱ ምስል ብቻ ነበር..ከነሙሉ ቁመናው ፤
አቋሙ ፤ መልኩ የማውቀው አንድ ሰው ቢኖር እሱ ብቻ ነበር፡፡ አሁን አሁን ሳስበው
ይገርመኛል...እኔም ልክ ዕዳ እንዳለበት አድርጌ ነበር የማስበው፡፡ከሳምንት አሳልፎ የመጣ ጊዜ
አኮርፈዋለሁ፣እነጫነጭበታለሁ፣የማለቅስበት ጊዜ ሁሉ አለ..ታዲያ ለምኖኝ
ተለማምጦኝ፤በስጦታ ደልሎኝ ይታረቀኛል፡፡
ከዛ ልክ 10ረኛ ክፍል እንደጨረስኩ እሱ የሚሰራበት መስሪያ ቤት ሙሉ በሙሉ ወደአዲስ አበባ ቀየረው፡፡እዛ ከገባ ደግሞ በወር አንድ ቀን እንኳን መጥቶ ሊጠይቀኝ ይከብደዋል፡፡ጭንቅ ሆነ ፤ሲያማክረኝ አበድኩበት..ሌላ ስራ እዛው ሻሸመኔ ለማግኘት ቢጥርም በፍጥነት ሊሳካለት አልቻለም፡፡ከዛ አብሬህ እሄዳለው አልኩት... ይገርምሀል የተደሰተው መደሰት ልነግርህ አልችልም፡፡ለካ በፊቱንም እሱ እሺ አትለኝም ብሎ ፈርቶ እንጄ ፍላጎቱ እንደዛ ነበር፡፡
ከዛ ተያይዘን ወደ አዲስ አበባ ሄድን፡፡ እንደእድል ሆኖ ደግሞ የሚሰራበት መስሪያ ቤት ሁለት ክፍል መኖሪያ ቤት ከነሙሉ ዕቃው ሰጥቶት ስለነበርን ያለችግር ኑሮን ጀመርን፡፡ የ11ኛ ክፍልም ትምህርቴንም እዛው ቀጠልኩ... ኮንትራት ታክሲ ይዞልኝ ከቤት እየተመላለስኩ ማለት ነው፡፡››
ንግግሯን አቋረጠችና እጇን ሚሪንዳ ወደ ያዘው ብርጭቆ ሰዳ በማንሳት አንዴ ገርገጭ አድርጋ ጉሮሮዋን አራሰችና‹‹ታዲ››ብላ ጠራችው
‹‹አቤት..፡፡››
<<ወሬዬ አልሰለቸህም አይደል...ይቅርታ ይሄን ታሪክ ከጀመርኩ ለማሳጠር ስለሚከብደኝ ነው...፡፡››
‹‹ኧረ ቀጥይ በጣም ተመስጬ ነው እያዳመጥኩሽ ያለሁት... ከፈለግሽ እስከነገም ቢሆን አዳምጥሻለሁ፡፡›› አላትና አንድ ሌላ ቢራ እንድትጨምርለት ለአስተናጋጇ በምልክት ነግሯት ትኩረቱን ወደ ጽዮን መለሰ፡፡
ቀጠለች‹‹....ከዛ በየቀኑ አብሬው እየኖርኩ... አብሬው እያደርኩ ...ትምህርቴን እየተማርኩ አስደሳች ህይወት መኖር ጀመርኩ፡፡ ይገርምሀል እድሜዬ 18 ወይም 19 አካባቢ ደርሶ ትልቅ ልጃገረድ ሆኜ እያለሁ እንኳን እሱ ምኔ እንደሆነ ?በምንስ ሂሳብ አብሬው እንደምኖር ? ለአንድም ቀን አስቤበት እና ተጨንቄበት አላውቅም ነበር፡፡ለምንስ እጨነቃለሁ... ለእኔ እሱ ማለት መላ ነገሬ ነው፤እናት አባቴ አክስት አጐቴ ነው…እሱ ስላለኝ ነው ስለምንም ጉዳይ የማልጨነቀው..
አባቴ ውትድርና ብሎ እንደወጣ ይሙት
አይሙት ሳይታወቅ በዛው ቢቀርም አልፎ አልፎ ባጋጣሚ ከማስታወስ ውጭ እሱን እያሰብኩ በሀዘን ተክዤ አላውቅም፤ ስለእናቴም አንዳንዴ እንኳን
እንደው ባገኘዋት ብዬ ማስበው ያኔ እንደው
በዛ ጮርቃ እድሜዬ ጡት እንኳን በደንብ ጠብቼ ሳልጠግብ ለአባቴ ጥላኝ እብስ ያለችው ምን አጋጥሞት ይሆን . ?.አባቴስ ምን
ያህል ቢበድላት ነው…?በጣም ቢመራት
እንኳን እንዴት ይዛኝ ለመሄድ ሳትሞክር
....?.እነዚህን የመሳሰሉትን የዕድሜ ልክ ጥያቄዎቼን እንድትመልስልኝ ብዬ እንጂ
እናትነቷ አጓጉቶኝ ..
እንክብካቤዋ ናፍቆኝ
አልነበረም፡፡
ደደፎ ሁሉን ነገር ነበር የሚሰጠኝ፤ምንም ያጣሁት ምንም የጎደለብኝ ነገር አልነበረም ፡፡ እንዳልኩት ሆኖ ነው፤ የጠየቅኩትን ሰጥቶኝ ፤የፈለግኩትን ገዝቶልኝ ነው፡፡ሲጠራኝ እንኳን በስሜ አይደለም.. ኪያ ነበር የሚለኝ ..<ኪያ
>ማለት የኦሮሚኛ ቃል ሲሆን ወደ አማርኛ ሲመለስ‹ የእኔ፤ የግሌ›› ማለት ነው ትምህርቴን ስጨርስ በፍላጎቴ ያሬድ ገብቼ ፒያኖ እንዳጠና አመቻቸልኝ፡፡ጀመርኩ፤ሁለት ዓመት ከተማርኩ በኃላ ችግር ተፈጠረ፡፡ትዝ ይለኛል እሁድ ቀን ነው 8 ሰዓት አካባቢ.......
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
እስኪመጣ ድረስ ክፉኛ በናፍቆት እሰቃይ
ጀመር፡፡ ሳይደበዝዝ በውስጤ ተቀርጾ የቀረው
የእሱ ምስል ብቻ ነበር..ከነሙሉ ቁመናው ፤
አቋሙ ፤ መልኩ የማውቀው አንድ ሰው ቢኖር እሱ ብቻ ነበር፡፡ አሁን አሁን ሳስበው
ይገርመኛል...እኔም ልክ ዕዳ እንዳለበት አድርጌ ነበር የማስበው፡፡ከሳምንት አሳልፎ የመጣ ጊዜ
አኮርፈዋለሁ፣እነጫነጭበታለሁ፣የማለቅስበት ጊዜ ሁሉ አለ..ታዲያ ለምኖኝ
ተለማምጦኝ፤በስጦታ ደልሎኝ ይታረቀኛል፡፡
ከዛ ልክ 10ረኛ ክፍል እንደጨረስኩ እሱ የሚሰራበት መስሪያ ቤት ሙሉ በሙሉ ወደአዲስ አበባ ቀየረው፡፡እዛ ከገባ ደግሞ በወር አንድ ቀን እንኳን መጥቶ ሊጠይቀኝ ይከብደዋል፡፡ጭንቅ ሆነ ፤ሲያማክረኝ አበድኩበት..ሌላ ስራ እዛው ሻሸመኔ ለማግኘት ቢጥርም በፍጥነት ሊሳካለት አልቻለም፡፡ከዛ አብሬህ እሄዳለው አልኩት... ይገርምሀል የተደሰተው መደሰት ልነግርህ አልችልም፡፡ለካ በፊቱንም እሱ እሺ አትለኝም ብሎ ፈርቶ እንጄ ፍላጎቱ እንደዛ ነበር፡፡
ከዛ ተያይዘን ወደ አዲስ አበባ ሄድን፡፡ እንደእድል ሆኖ ደግሞ የሚሰራበት መስሪያ ቤት ሁለት ክፍል መኖሪያ ቤት ከነሙሉ ዕቃው ሰጥቶት ስለነበርን ያለችግር ኑሮን ጀመርን፡፡ የ11ኛ ክፍልም ትምህርቴንም እዛው ቀጠልኩ... ኮንትራት ታክሲ ይዞልኝ ከቤት እየተመላለስኩ ማለት ነው፡፡››
ንግግሯን አቋረጠችና እጇን ሚሪንዳ ወደ ያዘው ብርጭቆ ሰዳ በማንሳት አንዴ ገርገጭ አድርጋ ጉሮሮዋን አራሰችና‹‹ታዲ››ብላ ጠራችው
‹‹አቤት..፡፡››
<<ወሬዬ አልሰለቸህም አይደል...ይቅርታ ይሄን ታሪክ ከጀመርኩ ለማሳጠር ስለሚከብደኝ ነው...፡፡››
‹‹ኧረ ቀጥይ በጣም ተመስጬ ነው እያዳመጥኩሽ ያለሁት... ከፈለግሽ እስከነገም ቢሆን አዳምጥሻለሁ፡፡›› አላትና አንድ ሌላ ቢራ እንድትጨምርለት ለአስተናጋጇ በምልክት ነግሯት ትኩረቱን ወደ ጽዮን መለሰ፡፡
ቀጠለች‹‹....ከዛ በየቀኑ አብሬው እየኖርኩ... አብሬው እያደርኩ ...ትምህርቴን እየተማርኩ አስደሳች ህይወት መኖር ጀመርኩ፡፡ ይገርምሀል እድሜዬ 18 ወይም 19 አካባቢ ደርሶ ትልቅ ልጃገረድ ሆኜ እያለሁ እንኳን እሱ ምኔ እንደሆነ ?በምንስ ሂሳብ አብሬው እንደምኖር ? ለአንድም ቀን አስቤበት እና ተጨንቄበት አላውቅም ነበር፡፡ለምንስ እጨነቃለሁ... ለእኔ እሱ ማለት መላ ነገሬ ነው፤እናት አባቴ አክስት አጐቴ ነው…እሱ ስላለኝ ነው ስለምንም ጉዳይ የማልጨነቀው..
አባቴ ውትድርና ብሎ እንደወጣ ይሙት
አይሙት ሳይታወቅ በዛው ቢቀርም አልፎ አልፎ ባጋጣሚ ከማስታወስ ውጭ እሱን እያሰብኩ በሀዘን ተክዤ አላውቅም፤ ስለእናቴም አንዳንዴ እንኳን
እንደው ባገኘዋት ብዬ ማስበው ያኔ እንደው
በዛ ጮርቃ እድሜዬ ጡት እንኳን በደንብ ጠብቼ ሳልጠግብ ለአባቴ ጥላኝ እብስ ያለችው ምን አጋጥሞት ይሆን . ?.አባቴስ ምን
ያህል ቢበድላት ነው…?በጣም ቢመራት
እንኳን እንዴት ይዛኝ ለመሄድ ሳትሞክር
....?.እነዚህን የመሳሰሉትን የዕድሜ ልክ ጥያቄዎቼን እንድትመልስልኝ ብዬ እንጂ
እናትነቷ አጓጉቶኝ ..
እንክብካቤዋ ናፍቆኝ
አልነበረም፡፡
ደደፎ ሁሉን ነገር ነበር የሚሰጠኝ፤ምንም ያጣሁት ምንም የጎደለብኝ ነገር አልነበረም ፡፡ እንዳልኩት ሆኖ ነው፤ የጠየቅኩትን ሰጥቶኝ ፤የፈለግኩትን ገዝቶልኝ ነው፡፡ሲጠራኝ እንኳን በስሜ አይደለም.. ኪያ ነበር የሚለኝ ..<ኪያ
>ማለት የኦሮሚኛ ቃል ሲሆን ወደ አማርኛ ሲመለስ‹ የእኔ፤ የግሌ›› ማለት ነው ትምህርቴን ስጨርስ በፍላጎቴ ያሬድ ገብቼ ፒያኖ እንዳጠና አመቻቸልኝ፡፡ጀመርኩ፤ሁለት ዓመት ከተማርኩ በኃላ ችግር ተፈጠረ፡፡ትዝ ይለኛል እሁድ ቀን ነው 8 ሰዓት አካባቢ.......
✨ይቀጥላል✨
#Share #like and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍69❤13😁3