#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
የሰው ልጆች የህይወት ጉዞ ልክ እንደ ሸረሪት ድር ነው፡፡እርስ በርሱ የተቆላለፈ.. የተሳሰረ እና የተወሳሰበ፡፡
…ሶፊያ ዲያስፖራ ነች፡፡የኢትጵያውያን ሲያኮሩፉ ሆነ ፈጣን በሆነ የህይወት ጉዞ ወጤታማ መሆን ምኞት በልባቸው ሲፀነስባቸው ግን ደግሞ ያንን ወደ ተግባር
ለመመንዘር የእኔ የሚሏት ሀገራቸው ዕድልና
አጋጣሚውን አላመቻችላቸው ስትል በኩርፊያ መልክ ከሚከትሙባት ሀገረ አሜሪካ ተመልሳ ወደሀገር ቤት ከገባች ገና አራት ወር
አልሞላትም፡፡
የተመለሰችበት ምክንያት ወደ ሀገር ተመልሳ ልማቱን እንድታፋጥን መንግስታዊ ጥሪ ተደርጎላት አይደለም፤ የአሜርካ ኳኳታ ሰልችቷት እንጂ፡፡
የሀገሯ አየር፣የሀገሯ ሰው፣የሀገሯ ፍቅር ናፍቆት
እንጂ፡፡ግን ይሄን እንዲሁ ሰዎች ለምን ተመለሽ
ብለው ሲጠይቋት ምትመልላቸው መልስ
ነው፡፡ትክክለኛው ምክንያቷ ግን እሷ ብቻ ነች ምታውቀው፤ምህረትን ፍለጋ ነው የመጣችው፡፡የዕድሜ ልኳን ፀፀት ከልቧ ለማራገፍ የሚያግዛትን ይቅርታ ለማግኘት፤ግን ከመምጣቷ በፊት እንዳሰበችው መንገዶች ቀላል አልሆኑላትም፡፡ከፀፀት ደዌ ልትፈውሳት የምትችለዋን ሴት በቀላሉ መቅረብ አልቻለችም፡፡
ዶ/ር ሶፊያ ወደ ሀገር ቤት ከተመለሰች በኃላ አንድ ዓለምአቀፍ ግብረሰናይ ድርጅት ውስጥ ነው ተቀጥራ የምትሰራው፡፡ቋሚ የስራ ቦታዋ አዲስ አበባ ቢሆንም አሁን ወደ ሀዋሳ ለመሄድ ዝግጅት ላይ ነች ፡፡አንድ አለም አቀፍ ድርጅት ለሶስት ቀናት ባዘጋጀው ሴሚናር ላይ ለመሳተፍ ፡፡
ሁሉንም ዝግጅቴን አጠናቅቄያለሁ ብላ እንቅስቃሴ ልትጀምር ስትል ነበር ያላሰበችው እክል የገጠማት፡፡ከግቢው ሳትወጣ መኪናዋ ተበላሸባት፡፡እዛ ጠብራራ አለቃዋ ጋር ደውላ የገጠማትን ችግር በዙሪያ ጥምዝ አስረድታ ሌላ መኪና እንዲቃይርላት ለማሳመን አሰበች፡፡
ግን አስባ ሳትጨርስ ደከማትና ተወችው፡፡
ሴሚናሩ የሚጀምረው ደግሞ ነገ ጥዋት ነው፤ስለዚህ ዛሬ ገብታ ማደር አለባት፡፡
መካኒክ አስመጥታ ለማሰራትም የማይታሰብ
ነገር ነው፡፡ለዛ የሚሆን በቂ ጊዜ የላትም፡፡
በትራንስፖርት ለመሄድ ወሰነች፡፡በሻንጣ ይዛ
የነበረውን ልብስ ወደ ቤት መለሰችና አስፈላጊ የሆኑትን ብቻ ወደ ቦርሳዋ ቀነሰች፡፡ አንድ መኪና ያለው የቅርቧ የሆነ ሰው ጋር ደውላ ቃሊቲ መነኸሪያ ድረስ ስለሸኛት ሚኒባስ ተሳፍራ ወደ ሀዋሳ ጉዞ ጀመረች፡፡ቢሾፍቱን አልፈው ሞጆን ተጠምዝዘው ቆቃን ተሸግረው መቂ አካባቢ ሲደርሱ ረዳቱ ሂሳብ መሰብሰብ ጀመረ….፡፡
ዶ/ሶፊያ ጋር ደረሰ ‹‹ሂሳብ›› አላት፡፡ቦርሳዋን ከፈተች... ፈለገች... በረበረች.. የእጅ ቦርሳዋ የለም፡፡
ረዳቱ‹‹እህት ሂሳብ ››ሲል ጥያቄውን ደገመው፡፡
‹‹እዚ ውስጥ ነበር.. ቤት ረስቼው መጣሁ መሰለኝ››በጣም ደነገጠች፡፡ጠይም ፊቷ ላይ ላቧ ቸፍ አለባት፡፡
‹‹ገንዘብ አልያዝኩም..።››
‹‹ባክሽ ሙድ አትያዢ፡፡››
‹‹እውነቴን ነው፡፡ ሞባይሌም፣ገንዘቤም፣ የእጅ ቦርሳዬ ውስጥ ነበር..እዚህ ውስጥ የከተትኩት መስሎኝ ነበር፡፡››
‹‹እኔ ጭቅጭቅ አልፈልግም…ሂሳቤን ስጪኝ፡፡››ረዳቱ ፊት ነሳት፡፡
‹‹ወንድም አንዴ ሞባይል ብታውሰኝ››ስትል ከጎኗ የተቀመጠውን ወጣት ጠየቀችው፡፡ ጥቁር ቆዳ ጄኬት ለብሶ ጥቁር መነፅር ፊቱ ላይ የሰካ ደልደል ያለ ሰው ነው፡፡
‹‹ይቅርታ ባትሪ ዘግቷል››አላት፡፡ይሄንን የሰማው ከፊት ለፊት የነበሩ አንድ አዛውንት ሰጧት፡፡
ደወለች‹‹ሄሎ ሰኒ ..ሶፊያ ነኝ፡፡››
‹‹የእጅ ቦርሳዬ አለ..?እስቲ እይልኝ፡፡››
‹‹አዎ በናትሽ ....ባንክ ደብተሬም መታወቂያዬም ውስጡ ነው፡፡››
‹‹ምንም ብር አልያዝኩም፡፡››
‹‹ምን ማድረግ እደምችል አላውቅም፡፡ ብትልኪልኝ እራሱ እንዴት አወጣለሁ..? መታወቂያ የለኝም..፡፡››
‹‹በቃ ለማንኛውም ከፈለኩሽ ሚስኮል አደርግልሻለሁ..››ብላ ስልኩን ዘጋችና ለባለቤቱ በመመለስ ‹‹ወንድም ሀዋሳ የማውቃቸው ሰዎች አሉ፤ እንደደረስን እሰጥሀለሁ››ስትል መልሳ ወያላውን መለማመጥ ቀጠለች፡፡
‹‹ባክሽ ..ዝዋይ ላይ ትወርጂልኛለሽ››ውሳኔውን አሳወቃት፡፡
በጣም ተጨናነቀች፡፡አንገቷ ላይ ያንጠለጠለችው የእናቷን ማስታወሻ ሀብል ትዝ አላት፡፡ ከዚህ በላይ መጨነቅ እንደሌለባት ወሰነች ፤ሀብሉን የማስያዝ ሀሳብ መጣላት፡፡ ኔትወርኩ በመሀል ከሰራላት ለምታውቃቸው ሰዎች ደውላ መነኸሪያ እንዲጠብቋት በማድረግ ሀብሏን ታስለቅቃለች፡፡ እስከእዛ ግን እራሷን ከስቃይ ለማላቀቅ ወሰነች፡፡
ሀብሉን ከአንገቷ አወጣችና‹‹ እንካ ይሄንን ያዝ፡፡ ሀዋሳ ደርሰን ብርህን ስሰጥህ ትመልስልኛለህ፡፡››በማለት እጁ ላይ አስቀመጠችለት፡፡ መቼም ይሄ ሁሉ ተሳፋሪ እያየ አይክደኝም ስትል ተስፋ አደረገች፡፡
የሰጠችውን ሀብል በእጆቹ ላይ እያገላበጠ ፈተሸና‹‹ሲስቱ ..አርቴ እንዳይሆን ብቻ፡፡፡››አላት፡፡
‹‹ባክህ ሃያ አራት ካራት ሆኖ 14 ግራም ወርቅ ነው፤ይልቅ በጥንቃቄ ያዘው፡፡››አለችው፡፡ በዚህን ጊዜ ከጎኗ ተቀምጦ የነበረው
እስከአሁን ነገሮችን በዝምታ ሲከታተል የቆየው ባለ ጥቁር መነፅሩ ወጣት ሁለት ድፍን የመቶ ብር ኖት አወጣና ሠጣት፡፡
‹‹ክፈይና ሀብልሽን ተቀበይው፡፡ለእኔ እዛ ስትደርሺ ትሰጪኛለሽ፡፡››
የወጣቱን ንግግር የሰማው ረዳት ተበሳጨበት፡፡እጁ የገባውን ዕድል ነው የነጠቀው<<የሆነ ምጥማጥ መልክ..የእርጐ ዝንብ ››በውስጡ አጉረመረመ፡፡
‹‹እግዜር ይስጥልኝ፡፡አመሰግናለሁ፡፡››በማለት ተቀበለችውና ለወያላው ወርውራለት ሀብሏን ተቀበለች፡፡ሠማንያ ብር መለሰላት፡፡ መልሱን ለወጣቱ ስትሰጠው‹‹ለውሃ ምናምን መግዣ ይሆንሻል..ያዢው፡፡ አንድ ላይ ትመልሺልኛለሽ፡፡››
‹‹የት ድረስ ነው የምትሄደው?››
‹‹ሀዋሳ ድረስ፡፡››
‹‹እንደደረስን እሰጥሀለሁ፡፡››
‹‹በማግስቱም ልትሰጪኝ ትችያለሽ፡፡››
እስኪሪፕቶና ወረቀት ከቦርሳዋ አውጥታ ሙሉ ስሟን ፤ ምትሰራበትን ቦታ እና ሁለቱንም የስልክ ቁጥሮቿን ፅፋ አቀበለችው፡፡ተቀበላትና እስኪሪፕቶውን ከእጇ በመውሰድ ወረቀቱን ገልብጦ ባልተፃፈበት በኩል የራሱን ጻፈና አጣጥፎ አቀበላት፡፡››
‹‹ምንድነው?››
‹‹ሲመችሽ አንቺው ደውይና ትሰጪኛለሽ፡፡››
ግራ ገባት ‹‹ባልደውልልህስ..?ብሸውድህስ?››
‹‹ብትደውይም አይደንቀኝ ..ባትደውይም አይገርመኝም፡፡››
‹‹አልገባኝም..፡፡››
‹‹ሁለቱም የሰው ልጅ ባህሪዋች ናቸው፡፡››ብሎ ብዙም ማውራት እንዳልፈለገ በሚገልፅ ስሜት ፊቱን ወደመስታወቱ አዙሮ ውጭ ውጩን ማየት ጀመረ፡፡
‹‹ሀብታም ወይም የሀብታም ልጅ ቢጤ ነው መሰለኝ፡፡ለዛ ነው የሚንጠባረርብኝ፡፡›› ስትል በውስጧ አሰበች፡፡
‹‹አይ አሁን ይህቺን ሁለት መቶ ብር አበደርኩሽ ብሎ በጅንጀና ያደርቀኛል፡፡›› ስትል ገመተች፡፡ ቆዳውን አዋዶ የእሷን ትኩረት
ለመሳብ እንዳቀደ እርግጠኛ ሆናለች፡፡‹‹ወንዶች እንኳን ይህቺን አይነት መግቢያ መንገድ አግኝተው ቀርቶ ድሮም ድሮ ናቸው፡፡›.አለች በልቧ፡፡
ዝዋይ ደረሱና ሚኒባሷ ለሻይ እረፍት ቆመች፡፡ ተሳፋሪዎች ሁሉ ወረዱና ሚያስፈልጋቸውን ነገር ገዛዝተው በመመለስ ጉዞው ቀጠለ፡፡ እሷም ወርዳ ውሀና መስቲካ ገዝታ ነበር፡፡አንድ ውሃ እና አንድ መስቲካ እያቀበለችው ‹‹በብድር ብር የተገዛ ቢሆንም እስኪ ልጋብዝህ፡፡››አለችው፡፡
ውሀውን ተቀበለና‹‹ጣፋጭ ነገር አልወድም፤ለውሀው ግን አመሰግናለሁ፡፡ >> አላት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አምስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
የሰው ልጆች የህይወት ጉዞ ልክ እንደ ሸረሪት ድር ነው፡፡እርስ በርሱ የተቆላለፈ.. የተሳሰረ እና የተወሳሰበ፡፡
…ሶፊያ ዲያስፖራ ነች፡፡የኢትጵያውያን ሲያኮሩፉ ሆነ ፈጣን በሆነ የህይወት ጉዞ ወጤታማ መሆን ምኞት በልባቸው ሲፀነስባቸው ግን ደግሞ ያንን ወደ ተግባር
ለመመንዘር የእኔ የሚሏት ሀገራቸው ዕድልና
አጋጣሚውን አላመቻችላቸው ስትል በኩርፊያ መልክ ከሚከትሙባት ሀገረ አሜሪካ ተመልሳ ወደሀገር ቤት ከገባች ገና አራት ወር
አልሞላትም፡፡
የተመለሰችበት ምክንያት ወደ ሀገር ተመልሳ ልማቱን እንድታፋጥን መንግስታዊ ጥሪ ተደርጎላት አይደለም፤ የአሜርካ ኳኳታ ሰልችቷት እንጂ፡፡
የሀገሯ አየር፣የሀገሯ ሰው፣የሀገሯ ፍቅር ናፍቆት
እንጂ፡፡ግን ይሄን እንዲሁ ሰዎች ለምን ተመለሽ
ብለው ሲጠይቋት ምትመልላቸው መልስ
ነው፡፡ትክክለኛው ምክንያቷ ግን እሷ ብቻ ነች ምታውቀው፤ምህረትን ፍለጋ ነው የመጣችው፡፡የዕድሜ ልኳን ፀፀት ከልቧ ለማራገፍ የሚያግዛትን ይቅርታ ለማግኘት፤ግን ከመምጣቷ በፊት እንዳሰበችው መንገዶች ቀላል አልሆኑላትም፡፡ከፀፀት ደዌ ልትፈውሳት የምትችለዋን ሴት በቀላሉ መቅረብ አልቻለችም፡፡
ዶ/ር ሶፊያ ወደ ሀገር ቤት ከተመለሰች በኃላ አንድ ዓለምአቀፍ ግብረሰናይ ድርጅት ውስጥ ነው ተቀጥራ የምትሰራው፡፡ቋሚ የስራ ቦታዋ አዲስ አበባ ቢሆንም አሁን ወደ ሀዋሳ ለመሄድ ዝግጅት ላይ ነች ፡፡አንድ አለም አቀፍ ድርጅት ለሶስት ቀናት ባዘጋጀው ሴሚናር ላይ ለመሳተፍ ፡፡
ሁሉንም ዝግጅቴን አጠናቅቄያለሁ ብላ እንቅስቃሴ ልትጀምር ስትል ነበር ያላሰበችው እክል የገጠማት፡፡ከግቢው ሳትወጣ መኪናዋ ተበላሸባት፡፡እዛ ጠብራራ አለቃዋ ጋር ደውላ የገጠማትን ችግር በዙሪያ ጥምዝ አስረድታ ሌላ መኪና እንዲቃይርላት ለማሳመን አሰበች፡፡
ግን አስባ ሳትጨርስ ደከማትና ተወችው፡፡
ሴሚናሩ የሚጀምረው ደግሞ ነገ ጥዋት ነው፤ስለዚህ ዛሬ ገብታ ማደር አለባት፡፡
መካኒክ አስመጥታ ለማሰራትም የማይታሰብ
ነገር ነው፡፡ለዛ የሚሆን በቂ ጊዜ የላትም፡፡
በትራንስፖርት ለመሄድ ወሰነች፡፡በሻንጣ ይዛ
የነበረውን ልብስ ወደ ቤት መለሰችና አስፈላጊ የሆኑትን ብቻ ወደ ቦርሳዋ ቀነሰች፡፡ አንድ መኪና ያለው የቅርቧ የሆነ ሰው ጋር ደውላ ቃሊቲ መነኸሪያ ድረስ ስለሸኛት ሚኒባስ ተሳፍራ ወደ ሀዋሳ ጉዞ ጀመረች፡፡ቢሾፍቱን አልፈው ሞጆን ተጠምዝዘው ቆቃን ተሸግረው መቂ አካባቢ ሲደርሱ ረዳቱ ሂሳብ መሰብሰብ ጀመረ….፡፡
ዶ/ሶፊያ ጋር ደረሰ ‹‹ሂሳብ›› አላት፡፡ቦርሳዋን ከፈተች... ፈለገች... በረበረች.. የእጅ ቦርሳዋ የለም፡፡
ረዳቱ‹‹እህት ሂሳብ ››ሲል ጥያቄውን ደገመው፡፡
‹‹እዚ ውስጥ ነበር.. ቤት ረስቼው መጣሁ መሰለኝ››በጣም ደነገጠች፡፡ጠይም ፊቷ ላይ ላቧ ቸፍ አለባት፡፡
‹‹ገንዘብ አልያዝኩም..።››
‹‹ባክሽ ሙድ አትያዢ፡፡››
‹‹እውነቴን ነው፡፡ ሞባይሌም፣ገንዘቤም፣ የእጅ ቦርሳዬ ውስጥ ነበር..እዚህ ውስጥ የከተትኩት መስሎኝ ነበር፡፡››
‹‹እኔ ጭቅጭቅ አልፈልግም…ሂሳቤን ስጪኝ፡፡››ረዳቱ ፊት ነሳት፡፡
‹‹ወንድም አንዴ ሞባይል ብታውሰኝ››ስትል ከጎኗ የተቀመጠውን ወጣት ጠየቀችው፡፡ ጥቁር ቆዳ ጄኬት ለብሶ ጥቁር መነፅር ፊቱ ላይ የሰካ ደልደል ያለ ሰው ነው፡፡
‹‹ይቅርታ ባትሪ ዘግቷል››አላት፡፡ይሄንን የሰማው ከፊት ለፊት የነበሩ አንድ አዛውንት ሰጧት፡፡
ደወለች‹‹ሄሎ ሰኒ ..ሶፊያ ነኝ፡፡››
‹‹የእጅ ቦርሳዬ አለ..?እስቲ እይልኝ፡፡››
‹‹አዎ በናትሽ ....ባንክ ደብተሬም መታወቂያዬም ውስጡ ነው፡፡››
‹‹ምንም ብር አልያዝኩም፡፡››
‹‹ምን ማድረግ እደምችል አላውቅም፡፡ ብትልኪልኝ እራሱ እንዴት አወጣለሁ..? መታወቂያ የለኝም..፡፡››
‹‹በቃ ለማንኛውም ከፈለኩሽ ሚስኮል አደርግልሻለሁ..››ብላ ስልኩን ዘጋችና ለባለቤቱ በመመለስ ‹‹ወንድም ሀዋሳ የማውቃቸው ሰዎች አሉ፤ እንደደረስን እሰጥሀለሁ››ስትል መልሳ ወያላውን መለማመጥ ቀጠለች፡፡
‹‹ባክሽ ..ዝዋይ ላይ ትወርጂልኛለሽ››ውሳኔውን አሳወቃት፡፡
በጣም ተጨናነቀች፡፡አንገቷ ላይ ያንጠለጠለችው የእናቷን ማስታወሻ ሀብል ትዝ አላት፡፡ ከዚህ በላይ መጨነቅ እንደሌለባት ወሰነች ፤ሀብሉን የማስያዝ ሀሳብ መጣላት፡፡ ኔትወርኩ በመሀል ከሰራላት ለምታውቃቸው ሰዎች ደውላ መነኸሪያ እንዲጠብቋት በማድረግ ሀብሏን ታስለቅቃለች፡፡ እስከእዛ ግን እራሷን ከስቃይ ለማላቀቅ ወሰነች፡፡
ሀብሉን ከአንገቷ አወጣችና‹‹ እንካ ይሄንን ያዝ፡፡ ሀዋሳ ደርሰን ብርህን ስሰጥህ ትመልስልኛለህ፡፡››በማለት እጁ ላይ አስቀመጠችለት፡፡ መቼም ይሄ ሁሉ ተሳፋሪ እያየ አይክደኝም ስትል ተስፋ አደረገች፡፡
የሰጠችውን ሀብል በእጆቹ ላይ እያገላበጠ ፈተሸና‹‹ሲስቱ ..አርቴ እንዳይሆን ብቻ፡፡፡››አላት፡፡
‹‹ባክህ ሃያ አራት ካራት ሆኖ 14 ግራም ወርቅ ነው፤ይልቅ በጥንቃቄ ያዘው፡፡››አለችው፡፡ በዚህን ጊዜ ከጎኗ ተቀምጦ የነበረው
እስከአሁን ነገሮችን በዝምታ ሲከታተል የቆየው ባለ ጥቁር መነፅሩ ወጣት ሁለት ድፍን የመቶ ብር ኖት አወጣና ሠጣት፡፡
‹‹ክፈይና ሀብልሽን ተቀበይው፡፡ለእኔ እዛ ስትደርሺ ትሰጪኛለሽ፡፡››
የወጣቱን ንግግር የሰማው ረዳት ተበሳጨበት፡፡እጁ የገባውን ዕድል ነው የነጠቀው<<የሆነ ምጥማጥ መልክ..የእርጐ ዝንብ ››በውስጡ አጉረመረመ፡፡
‹‹እግዜር ይስጥልኝ፡፡አመሰግናለሁ፡፡››በማለት ተቀበለችውና ለወያላው ወርውራለት ሀብሏን ተቀበለች፡፡ሠማንያ ብር መለሰላት፡፡ መልሱን ለወጣቱ ስትሰጠው‹‹ለውሃ ምናምን መግዣ ይሆንሻል..ያዢው፡፡ አንድ ላይ ትመልሺልኛለሽ፡፡››
‹‹የት ድረስ ነው የምትሄደው?››
‹‹ሀዋሳ ድረስ፡፡››
‹‹እንደደረስን እሰጥሀለሁ፡፡››
‹‹በማግስቱም ልትሰጪኝ ትችያለሽ፡፡››
እስኪሪፕቶና ወረቀት ከቦርሳዋ አውጥታ ሙሉ ስሟን ፤ ምትሰራበትን ቦታ እና ሁለቱንም የስልክ ቁጥሮቿን ፅፋ አቀበለችው፡፡ተቀበላትና እስኪሪፕቶውን ከእጇ በመውሰድ ወረቀቱን ገልብጦ ባልተፃፈበት በኩል የራሱን ጻፈና አጣጥፎ አቀበላት፡፡››
‹‹ምንድነው?››
‹‹ሲመችሽ አንቺው ደውይና ትሰጪኛለሽ፡፡››
ግራ ገባት ‹‹ባልደውልልህስ..?ብሸውድህስ?››
‹‹ብትደውይም አይደንቀኝ ..ባትደውይም አይገርመኝም፡፡››
‹‹አልገባኝም..፡፡››
‹‹ሁለቱም የሰው ልጅ ባህሪዋች ናቸው፡፡››ብሎ ብዙም ማውራት እንዳልፈለገ በሚገልፅ ስሜት ፊቱን ወደመስታወቱ አዙሮ ውጭ ውጩን ማየት ጀመረ፡፡
‹‹ሀብታም ወይም የሀብታም ልጅ ቢጤ ነው መሰለኝ፡፡ለዛ ነው የሚንጠባረርብኝ፡፡›› ስትል በውስጧ አሰበች፡፡
‹‹አይ አሁን ይህቺን ሁለት መቶ ብር አበደርኩሽ ብሎ በጅንጀና ያደርቀኛል፡፡›› ስትል ገመተች፡፡ ቆዳውን አዋዶ የእሷን ትኩረት
ለመሳብ እንዳቀደ እርግጠኛ ሆናለች፡፡‹‹ወንዶች እንኳን ይህቺን አይነት መግቢያ መንገድ አግኝተው ቀርቶ ድሮም ድሮ ናቸው፡፡›.አለች በልቧ፡፡
ዝዋይ ደረሱና ሚኒባሷ ለሻይ እረፍት ቆመች፡፡ ተሳፋሪዎች ሁሉ ወረዱና ሚያስፈልጋቸውን ነገር ገዛዝተው በመመለስ ጉዞው ቀጠለ፡፡ እሷም ወርዳ ውሀና መስቲካ ገዝታ ነበር፡፡አንድ ውሃ እና አንድ መስቲካ እያቀበለችው ‹‹በብድር ብር የተገዛ ቢሆንም እስኪ ልጋብዝህ፡፡››አለችው፡፡
ውሀውን ተቀበለና‹‹ጣፋጭ ነገር አልወድም፤ለውሀው ግን አመሰግናለሁ፡፡ >> አላት፡፡
👍89❤9😁4🔥1
ምን እንደምትመልስለት በማሰላሰል ላይ ሳለች ከጃኬት ኪሱ ውስጥ አንድ በእንግሊዘኛ ቋንቋ የተፃፈ የፍልስፍና መፅሀፍ አውጥቶ ከፈተና ማንበብ ቀጠለ‹‹ምን አይነት ጉረኛ ገጠመኝ?››አለች በልቧ ‹‹አሁን ደግሞ ሀብታም ብቻ ሳልሆን ምሁርም ነኝ ለማለት ነው አይደል..?ሁለት ገፅ ሳያነብ መጽሀፉን መልሶ ከድኖ መቀባጠሩን መጀመሩ አይቀርም፡፡›› ከራሷ ጋር ተወራረደች፡፡አዳሚ ቱሉ ሲደርሱ ከሀያ ገጾች በላይ አንብቧል ፡፡ ገረሜታዋ ጨመረ፤ ተደነቀችበት፤ተቁነጠነጠች፡፡ከዚህ በፊት ተሰምቷት የማያውቀውን የመረሳትና የመገፋት ስሜት ተሰማት፡፡እንዲያወራት... ስለማንነቱ እንዲነግራት ተመኘች፡፡እሱ ንባቡን ቀጥሏል፡፡አርሲ ነገሌ ሲደርሱም ዓኖቹን ከመጽሀፉ አልነቀልም ነበር፡፡
‹‹ይህቺ ከተማ ምንድነች?››አለችው፤የከተማዋን ማንነት ሳታውቅ ቀርታ ሳይሆነ እንዲያወራት ስለፈለገች ነበር ጥያቄውን የሰነዘረችው፡፡
ከንባቡ አይኑን ሳይነቅል‹‹ሲኦል ሳትሆን አትቀርም››አላት ፡፡
‹‹ወይኔ ምን አለበት አሁን አንድ ሺህ ብር ባገኝ፤ይሄው ሁለት መቶው ያበደርከኝ ነው ፤ይሄ ስምንት መቶ ብሩ ደግሞ ሻይ ጠጣበት ብዬ አፍንጫው ላይ ወረውርለትና እንዳበሸቀኝ አበሽቀው ነበር፡፡››ስትል በውስጧ ድምፅ አልባ ማጉረምረም አጉረመረመች፡፡ የሆነ ሀሳብ መጣላት፡፡ በቃ ቀልቡን ከገባበት መመሰጥ እንዴት መንጥቃ እንደምትዋጣው ተገለጸላት፡፡ እስካሁንም እንዴት እንዳላሰበችው ደነቃት፡፡
‹‹ባይ ዘዌይ ዲያስፖራ ነኝ ፡፡በቅርብ ነው ከአሜሪካ የመጣሁት፡፡››ከጎሬው የምታወጣበትን ወጥመዷን ወረወረች፡፡
ካቀረቀረበት ንባቡ ቀና ብሎ ፊት ለፊት አያት፡፡ ፈገገች ፡፡እንደገመተችው ኢትጵያውያን ከአሜሪካ ለመጣ ሰው ያላቸው ክብርና ጉጉት የሚገርም አይነት ነው፡፡አንድ ሰው ከገነት ነው የመጣሁት ከሚል ይልቅ ከአሜሪካ ነው የመጣሁት ቢል የበለጠ ቀልብ ይስባል፡፡ ከአሜሪካ ከመጣ ጓደኛዬ ጋር ስዝናና ቆየሁ ብሎ ማውራት እንኳን ትልቅ ዝናን ያስገኛል፡፡ ይሄንን ስነ ልቦና ስለምታውቅ ነው የልጁን ቀልብ ለመሳብ ለሳእታት ያልተሳካላትን በዚህ ዘዴ ለሞከር የወሰነችው፡፡
<< እና ምን ይጠበስ? ››አላትና ወደ ንባቡ ተመለሰ ፡፡በጣም ተደነቀች፡፡በእፍረት ኩምሽሽ ነው ያለችው፡፡ምን አይነት ሰው ነው ?:: እንኳን ኢትዬጵያ አሜሪካም እንዲህ አይነት ሰው አጋጥሟት አያውቅም..‹‹ይሄን ሰውዬማ በደንብ ማወቅ አለብኝ፡፡›› ለራሷ ቃል ገባች፡፡
ሻሸመኔን አለፉ..ሀዋሳ ገቡ..ጥቁር ውሀ አካባቢ ሲደርሱ መጽሀፉን ሊጨርስ አስር ገፅ ያህል ብቻ ቀርቶት ነበር፡፡
መነኻሪያ ከመድረሳቸው በፊት አንድ አሮጊት ‹‹ወራጅ›› አሉ፡፡ሚኒባሷ ሃምሳ ሜትር አካባቢ ከተጓዘች በኃላ ቆመች፤አሮጊቷ ሲወርዱ አብሻቂው ወጣትም ድንገት ተነሳ…‹‹እንዴ ልትወርድ ነው ?>>
‹‹አዎ... እዚህ አካባቢ ጉዳይ አለኝ >>አላት፡፡
‹‹እደውልልሀለው››
‹‹እሺ››ብሏት መውረድ ጀመረ…፡፡ተሳፋሪው ምን ይለኛል ብላ ሳትጨነቅ‹‹ግን ስምህ ማን ነበር?››ብላ ጠየቀችው ፡፡
‹‹ደስ ባለሽ ስም ጥሪኝ፤ችግር የለውም ››ብሏት መንገዱን ቀጠለ፡፡ሚኒባሷም ተንቀሳቀሰች፡፡መነኻሪያ ወረደችና ኮንትራት ባጃጅ ይዛ ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቷ ወደሚገኝበት ስፍራ ሄደች ፡፡ሁሉም ችግሯ ወዲያው ተፈታላት፡፡ የሚስፈልጋትን ያህል ብር ከመስሪያ ቤቷ ተሰጣት፡፡ለጊዜው የምትጠቀምበት ስልክም ከነሲሙ ገዛች፡፡
ከዛም ወደ ተያዘላት መኝታ ክፍል ገብታ ሻወር ከወሳሰደችና ከተረጋጋገች በኃለ ለዛ ብሽቅ ልጅ ደውላለት ብሩን ልትሰጠውና ልታወራው ፈለገች፡፡ ቦርሳዋን አወጣችና ስልክ ቁጥሩን የጻፈበትን ወረቀት አወጣች እና ገልጣ አየችው፡፡ ደነገጠች..ሸውዷታል፡፡ቁጥር የለውም... ጹሁፍ ነው፡፡
<< ተመሳሳይ ችግር የገጠመው ሰው ስታገኚ ለእሱ አድርጊ...የዛኔ ለእኔ ብድርሽን እደከፈልሽ ይቆጠራል፡፡ >>
ይላል ወረቀቱ ላይ የተወላት ፅሁፍ፡፡‹‹ብሽቅ›› አለች፡፡
‹‹እንዴት በወቅቱ ገልጬ ሳላነበው ?›› በራሷ ላይ ተበሳጨች፡፡እርግጥ አጣጥፎ ነበር የሰጣት ፤ቢሆንም ገልጣ ማረጋገጥ ነበረባት፡፡ ለሊቱን ሙሉ በተኛችበት ጊዜያቶች እንኳን ልትረሳው አልቻለችም፡፡
ለሦስት ቀን የተካሄደው ሴሚናር ተጠናቀቀ፡፡
በሀዋሳ ቆይታዋ ላይ ሌላ ሦስት ቀን ጨምራ
ቅ/መስሪያ ቤቱ በመደበላት መኪና በመጠቀም የሀዋሳን ከተማ ጎዳናዎች
በመዞር ብታስስም ልጁ ግን ሊገኝ አልቻለም፡፡
ይበልጥ በፈለገችው ቁጥር ይበልጥ እየናፈቃት መጣ፡፡ ለአመታት አብሯት የኖረ
በጣም የቅርቧ ሰው ድንገት ተሰውሮ የጠፋባት ያህል ነው አዕምሮዋ እርብሽብሽ
ያለባት፡፡ምርጫ ስላልነበራት በቅሬታ እንደተሞላች ወደ አዲስአባዋ ተመለሰች፡፡
✨ይቀጥላል✨
አሁንም ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ አበረታቱን ቤተሰቦች 5 እና ከዛ በላይ #ሰብስክራይብ ካገኘን ነገ ሁለት ክፍል ይለቀቃል። ቃላችንን አስጠብቁን👍
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹ይህቺ ከተማ ምንድነች?››አለችው፤የከተማዋን ማንነት ሳታውቅ ቀርታ ሳይሆነ እንዲያወራት ስለፈለገች ነበር ጥያቄውን የሰነዘረችው፡፡
ከንባቡ አይኑን ሳይነቅል‹‹ሲኦል ሳትሆን አትቀርም››አላት ፡፡
‹‹ወይኔ ምን አለበት አሁን አንድ ሺህ ብር ባገኝ፤ይሄው ሁለት መቶው ያበደርከኝ ነው ፤ይሄ ስምንት መቶ ብሩ ደግሞ ሻይ ጠጣበት ብዬ አፍንጫው ላይ ወረውርለትና እንዳበሸቀኝ አበሽቀው ነበር፡፡››ስትል በውስጧ ድምፅ አልባ ማጉረምረም አጉረመረመች፡፡ የሆነ ሀሳብ መጣላት፡፡ በቃ ቀልቡን ከገባበት መመሰጥ እንዴት መንጥቃ እንደምትዋጣው ተገለጸላት፡፡ እስካሁንም እንዴት እንዳላሰበችው ደነቃት፡፡
‹‹ባይ ዘዌይ ዲያስፖራ ነኝ ፡፡በቅርብ ነው ከአሜሪካ የመጣሁት፡፡››ከጎሬው የምታወጣበትን ወጥመዷን ወረወረች፡፡
ካቀረቀረበት ንባቡ ቀና ብሎ ፊት ለፊት አያት፡፡ ፈገገች ፡፡እንደገመተችው ኢትጵያውያን ከአሜሪካ ለመጣ ሰው ያላቸው ክብርና ጉጉት የሚገርም አይነት ነው፡፡አንድ ሰው ከገነት ነው የመጣሁት ከሚል ይልቅ ከአሜሪካ ነው የመጣሁት ቢል የበለጠ ቀልብ ይስባል፡፡ ከአሜሪካ ከመጣ ጓደኛዬ ጋር ስዝናና ቆየሁ ብሎ ማውራት እንኳን ትልቅ ዝናን ያስገኛል፡፡ ይሄንን ስነ ልቦና ስለምታውቅ ነው የልጁን ቀልብ ለመሳብ ለሳእታት ያልተሳካላትን በዚህ ዘዴ ለሞከር የወሰነችው፡፡
<< እና ምን ይጠበስ? ››አላትና ወደ ንባቡ ተመለሰ ፡፡በጣም ተደነቀች፡፡በእፍረት ኩምሽሽ ነው ያለችው፡፡ምን አይነት ሰው ነው ?:: እንኳን ኢትዬጵያ አሜሪካም እንዲህ አይነት ሰው አጋጥሟት አያውቅም..‹‹ይሄን ሰውዬማ በደንብ ማወቅ አለብኝ፡፡›› ለራሷ ቃል ገባች፡፡
ሻሸመኔን አለፉ..ሀዋሳ ገቡ..ጥቁር ውሀ አካባቢ ሲደርሱ መጽሀፉን ሊጨርስ አስር ገፅ ያህል ብቻ ቀርቶት ነበር፡፡
መነኻሪያ ከመድረሳቸው በፊት አንድ አሮጊት ‹‹ወራጅ›› አሉ፡፡ሚኒባሷ ሃምሳ ሜትር አካባቢ ከተጓዘች በኃላ ቆመች፤አሮጊቷ ሲወርዱ አብሻቂው ወጣትም ድንገት ተነሳ…‹‹እንዴ ልትወርድ ነው ?>>
‹‹አዎ... እዚህ አካባቢ ጉዳይ አለኝ >>አላት፡፡
‹‹እደውልልሀለው››
‹‹እሺ››ብሏት መውረድ ጀመረ…፡፡ተሳፋሪው ምን ይለኛል ብላ ሳትጨነቅ‹‹ግን ስምህ ማን ነበር?››ብላ ጠየቀችው ፡፡
‹‹ደስ ባለሽ ስም ጥሪኝ፤ችግር የለውም ››ብሏት መንገዱን ቀጠለ፡፡ሚኒባሷም ተንቀሳቀሰች፡፡መነኻሪያ ወረደችና ኮንትራት ባጃጅ ይዛ ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቷ ወደሚገኝበት ስፍራ ሄደች ፡፡ሁሉም ችግሯ ወዲያው ተፈታላት፡፡ የሚስፈልጋትን ያህል ብር ከመስሪያ ቤቷ ተሰጣት፡፡ለጊዜው የምትጠቀምበት ስልክም ከነሲሙ ገዛች፡፡
ከዛም ወደ ተያዘላት መኝታ ክፍል ገብታ ሻወር ከወሳሰደችና ከተረጋጋገች በኃለ ለዛ ብሽቅ ልጅ ደውላለት ብሩን ልትሰጠውና ልታወራው ፈለገች፡፡ ቦርሳዋን አወጣችና ስልክ ቁጥሩን የጻፈበትን ወረቀት አወጣች እና ገልጣ አየችው፡፡ ደነገጠች..ሸውዷታል፡፡ቁጥር የለውም... ጹሁፍ ነው፡፡
<< ተመሳሳይ ችግር የገጠመው ሰው ስታገኚ ለእሱ አድርጊ...የዛኔ ለእኔ ብድርሽን እደከፈልሽ ይቆጠራል፡፡ >>
ይላል ወረቀቱ ላይ የተወላት ፅሁፍ፡፡‹‹ብሽቅ›› አለች፡፡
‹‹እንዴት በወቅቱ ገልጬ ሳላነበው ?›› በራሷ ላይ ተበሳጨች፡፡እርግጥ አጣጥፎ ነበር የሰጣት ፤ቢሆንም ገልጣ ማረጋገጥ ነበረባት፡፡ ለሊቱን ሙሉ በተኛችበት ጊዜያቶች እንኳን ልትረሳው አልቻለችም፡፡
ለሦስት ቀን የተካሄደው ሴሚናር ተጠናቀቀ፡፡
በሀዋሳ ቆይታዋ ላይ ሌላ ሦስት ቀን ጨምራ
ቅ/መስሪያ ቤቱ በመደበላት መኪና በመጠቀም የሀዋሳን ከተማ ጎዳናዎች
በመዞር ብታስስም ልጁ ግን ሊገኝ አልቻለም፡፡
ይበልጥ በፈለገችው ቁጥር ይበልጥ እየናፈቃት መጣ፡፡ ለአመታት አብሯት የኖረ
በጣም የቅርቧ ሰው ድንገት ተሰውሮ የጠፋባት ያህል ነው አዕምሮዋ እርብሽብሽ
ያለባት፡፡ምርጫ ስላልነበራት በቅሬታ እንደተሞላች ወደ አዲስአባዋ ተመለሰች፡፡
✨ይቀጥላል✨
አሁንም ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ አበረታቱን ቤተሰቦች 5 እና ከዛ በላይ #ሰብስክራይብ ካገኘን ነገ ሁለት ክፍል ይለቀቃል። ቃላችንን አስጠብቁን👍
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍71👏8❤6😁1
#ቅብጥብጡ_ውሻ
የት እንዳነበብኳት ባላስታውስም ከረጅም ጊዜ በፊት ያነበብኳት አንዲት አጭር ታሪክ ትዝ አለችኝ፡፡ አስተምራኝ አልፋለች፣ ዛሬም ባሰብኳት ቁጥር ታስተምረኛለች፡፡ የአንድ ሰውና የውሻው አጭር ታሪክ ነው፡፡
በገጠራማው አካባቢ የሚኖር አንድ ሰው ከቤቱ ወጥቶ ወደ 30 ደቂቃ የሚፈጅ የእግር ጉዞ ካደረገ በኋላ መድረስ ወደሚገባው የወዳጁ ቤት ደረሰ፡፡ ከእሱ ጋር እሱ በሄደበት ሁሉ የሚከተለው በጣም የሚወደው ውሻው እንደተለመደው ተከትሎት መጥቷል፡፡ ሰውየው ወዳጁ ቤት ሲደርስ ከወዳጁ ጋር ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ ወዳጁ፣ “ያ ሁልጊዜ በሄድክበት ሁሉ የሚከተልህ ውሻህስ የት አለ?” ብሎ ገና ከመጠየቁ ውሻው እያለከለከና በውኃ ጥም ለሃጩን እያዝረከረከ ከባለቤቱ ጀርባ ከተፍ አለ፡፡
የዚህ ሰው ወዳጅ የሰውየውን አለመድከም ከውሻው ማለክለክ ጋር አነጻጸረና፣ “ውሻህን ምን አድርገኸው ነው እንደዚህ የደከመው፡፡ አንተ ምንም የድካ ስሜት አይታይብህም፣ እሱ ግን በጣም ደክሟል” አለው፣ ልክ በውሻው ላይ እንደጨከነበትና ችላ እንዳለው አይነት ስሜት በሚሰጥ ሁኔታ፡፡
የውሻውም ባለቤት ይህ የለመደውና በሄደበት ሁሉ ሰዎች የሚጠይቁት ጥያቄ በመሆኑ ብዙም ሳይገረም በውስጡ አቀባብሎ ያለውን መልስ መለሰለት፣ “የሚገርምህ ነገር ሁለታችን ከቤት ተነስተን እኩል መንገድ ነው የመጣነው፡፡ በእኔና በእሱ መካከል ያለው ልዩነት እኔ ቀጥ ብዬና ተረጋግቼ ነው የመጣሁት፣ እሱ ግን አንዴ ወደ ግራ፣ አንዴ ደግሞ ወደ ቀኝ ሲባዝን፤ አንዴ አንድን ነገር ሲያባርር፣ እንዴ ደግሞ ቆም ብሎ መሬቱን እያሸተተ አንድን ነገር አገኛለሁ ብሎ ሲቆፍ፣ እኔ ስርቅበት ደግሞ ለመድረስ ሲሮጥ . . . ሁል ጊዜ እሱን የሚያደክመው ይህ ቅብጥብጥ ባህሪው ነው”፡፡
ለካ ያለመጠን የሚያደክመን መንገዳችን ብቻውን አይደለም፣ ለካ የሚያዝለን ስራችን ብቻውን አይደለም፣ ለካ በቀኑ መጨረሻ ላይ ዝልፍልፍ የሚያደርገን የቀኑ ዋና ዓላማችን አይደለም፣ ለካ በኑሮ ድክም ያልነው በተለመደው የኑሮ ሂደት አይደለም፡፡ እኛን የሚያደክመንና ዝለት ውስጥ የሚከተን በመንገዳችን ላይ በማያገባን ነገር እየገባን ወዲህና ወዲያ የምንለው ነገር ነው፡፡
ይህ እውነት የገባኝ ቀን . . .
ስለማያገባኝ ሰው ማውራት አቆምኩኝ፣ በማያገባኝ ስፍራ መገኘት ተውኩኝ፣ ምንም ለውጥ በማያመጣ ነገር ላይ መከራከርን ጣልኩት፣ ምንም ተጽእኖ ከማላመጣለት ሰው ጋር መነታረክን ተወት አደረኩኝ፣ ድምዳሜ ላይ ስደርስ ምንም ፋይዳ የማያመጣልኝን ጉዳይ ማሰላሰል እርግፍ አደረኩኝ . . . በአጭሩ የማደርገው ነገር ሁሉ ከዋናው የህይወቴ ዓላማና እሴት ጋር የመጣጣሙን ጉዳይ ማሰብ መኖር ጀመርኩኝ፡፡
ይህንን ያደረኩኝ ጊዜ ብዙ ሸክም ከላዬ ላይ የተነሳ ያህል እርምጃዬ ቀለለኝ፣ ምክንያት-የለሹ የድካም ስሜት ተወኝ፣ የጀመርኩትን ግቤን ጥጉ የማድረስ ጉልበት አገኘሁኝ! ለካ እኔንም ልክ እንደ ቅብጥብጡ ውሻ ያደከመኝ ቀጥታው ሳይሆን ግራ-ቀኙ እና መለስ-ቀለሱ ነው!
🔘በዶ/ር እዮብ ማሞ🔘
ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ አበረታቱን እንጂ ትላንት
5 ሰው ብለን ማንም #ሰብስክራይብ አላደረገም እስከ ማታ 5 ሰው #እጠብቃለሁ
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
የት እንዳነበብኳት ባላስታውስም ከረጅም ጊዜ በፊት ያነበብኳት አንዲት አጭር ታሪክ ትዝ አለችኝ፡፡ አስተምራኝ አልፋለች፣ ዛሬም ባሰብኳት ቁጥር ታስተምረኛለች፡፡ የአንድ ሰውና የውሻው አጭር ታሪክ ነው፡፡
በገጠራማው አካባቢ የሚኖር አንድ ሰው ከቤቱ ወጥቶ ወደ 30 ደቂቃ የሚፈጅ የእግር ጉዞ ካደረገ በኋላ መድረስ ወደሚገባው የወዳጁ ቤት ደረሰ፡፡ ከእሱ ጋር እሱ በሄደበት ሁሉ የሚከተለው በጣም የሚወደው ውሻው እንደተለመደው ተከትሎት መጥቷል፡፡ ሰውየው ወዳጁ ቤት ሲደርስ ከወዳጁ ጋር ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ ወዳጁ፣ “ያ ሁልጊዜ በሄድክበት ሁሉ የሚከተልህ ውሻህስ የት አለ?” ብሎ ገና ከመጠየቁ ውሻው እያለከለከና በውኃ ጥም ለሃጩን እያዝረከረከ ከባለቤቱ ጀርባ ከተፍ አለ፡፡
የዚህ ሰው ወዳጅ የሰውየውን አለመድከም ከውሻው ማለክለክ ጋር አነጻጸረና፣ “ውሻህን ምን አድርገኸው ነው እንደዚህ የደከመው፡፡ አንተ ምንም የድካ ስሜት አይታይብህም፣ እሱ ግን በጣም ደክሟል” አለው፣ ልክ በውሻው ላይ እንደጨከነበትና ችላ እንዳለው አይነት ስሜት በሚሰጥ ሁኔታ፡፡
የውሻውም ባለቤት ይህ የለመደውና በሄደበት ሁሉ ሰዎች የሚጠይቁት ጥያቄ በመሆኑ ብዙም ሳይገረም በውስጡ አቀባብሎ ያለውን መልስ መለሰለት፣ “የሚገርምህ ነገር ሁለታችን ከቤት ተነስተን እኩል መንገድ ነው የመጣነው፡፡ በእኔና በእሱ መካከል ያለው ልዩነት እኔ ቀጥ ብዬና ተረጋግቼ ነው የመጣሁት፣ እሱ ግን አንዴ ወደ ግራ፣ አንዴ ደግሞ ወደ ቀኝ ሲባዝን፤ አንዴ አንድን ነገር ሲያባርር፣ እንዴ ደግሞ ቆም ብሎ መሬቱን እያሸተተ አንድን ነገር አገኛለሁ ብሎ ሲቆፍ፣ እኔ ስርቅበት ደግሞ ለመድረስ ሲሮጥ . . . ሁል ጊዜ እሱን የሚያደክመው ይህ ቅብጥብጥ ባህሪው ነው”፡፡
ለካ ያለመጠን የሚያደክመን መንገዳችን ብቻውን አይደለም፣ ለካ የሚያዝለን ስራችን ብቻውን አይደለም፣ ለካ በቀኑ መጨረሻ ላይ ዝልፍልፍ የሚያደርገን የቀኑ ዋና ዓላማችን አይደለም፣ ለካ በኑሮ ድክም ያልነው በተለመደው የኑሮ ሂደት አይደለም፡፡ እኛን የሚያደክመንና ዝለት ውስጥ የሚከተን በመንገዳችን ላይ በማያገባን ነገር እየገባን ወዲህና ወዲያ የምንለው ነገር ነው፡፡
ይህ እውነት የገባኝ ቀን . . .
ስለማያገባኝ ሰው ማውራት አቆምኩኝ፣ በማያገባኝ ስፍራ መገኘት ተውኩኝ፣ ምንም ለውጥ በማያመጣ ነገር ላይ መከራከርን ጣልኩት፣ ምንም ተጽእኖ ከማላመጣለት ሰው ጋር መነታረክን ተወት አደረኩኝ፣ ድምዳሜ ላይ ስደርስ ምንም ፋይዳ የማያመጣልኝን ጉዳይ ማሰላሰል እርግፍ አደረኩኝ . . . በአጭሩ የማደርገው ነገር ሁሉ ከዋናው የህይወቴ ዓላማና እሴት ጋር የመጣጣሙን ጉዳይ ማሰብ መኖር ጀመርኩኝ፡፡
ይህንን ያደረኩኝ ጊዜ ብዙ ሸክም ከላዬ ላይ የተነሳ ያህል እርምጃዬ ቀለለኝ፣ ምክንያት-የለሹ የድካም ስሜት ተወኝ፣ የጀመርኩትን ግቤን ጥጉ የማድረስ ጉልበት አገኘሁኝ! ለካ እኔንም ልክ እንደ ቅብጥብጡ ውሻ ያደከመኝ ቀጥታው ሳይሆን ግራ-ቀኙ እና መለስ-ቀለሱ ነው!
🔘በዶ/ር እዮብ ማሞ🔘
ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ አበረታቱን እንጂ ትላንት
5 ሰው ብለን ማንም #ሰብስክራይብ አላደረገም እስከ ማታ 5 ሰው #እጠብቃለሁ
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍74❤5🥰4
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሁሴን ወደ ሲዊዘርላንድ ሊበር ከ3ዐ ሰዓት ያነሰ ጊዜ ቢቀረውም ከመሄዱ በፊት የውብዳርን እና ልጆቹን መሰናበት ስለፈለገ ወደ እነሱ እየሄደ ነው፡፡ ትናንትና የሽኝት ዝግጅቱ ላይ ልጆቹን ይዛ እንድትገኝ በስልክ ደውሎ ነግሯት ነበር፤እሷም እንደምትገኝ ቃሏን ስጥታው ነበር፤ነገር ግን አልተገኘችም፡፡ ያው ከድሮ ባሏ እና ከጣውንቷ ጋር ፊት ለፊት ተገናኝቶ መፍጠጥ ደብሯት እንደሆነ ስለገባው ባለመምጣቷ ብዙም ቅር አላለውም፡፡
እንደውም በተቀራኒው ከስልክ ግንኙነት ውጭ በአካል ሳያገኛት አራት ወራቶች በማሳለፉ ፀፀት ነገር ሽው ብሎበታል፡፡
ዛሬም እንደሚመጣ ሲደውልላት ቀዝቀዝ ባለ ስሜት ነበር ‹‹..በቃ ና... ቤት ነኝ፡፡››ያለችው፡፡
ደርሶ የመኪናውን ክላክስ ሲያስጮህ ዘበኛው የውጪን በራፍ ከፈተለት፡፡ መኪናውን ወደ ግቢ ውስጥ አስገባና ምቹ ቦታ ፈልጐ በማቆም ሞተሩን አጥፍቶ ወደ ውስጥ ገባ፡፡የውብዳር ሳሎን ብቻዋን ቁጭ ብላ ነበር፡፡
ሲያያት ደነገጠ.፡፡ጉስቁልቁል ብላለች፡፡የሆነ ጭምድድ ያለ ቢጃማ ቀሚስ ለብሳለች፣የፀጉሯ መንጨፍረር በየጫካው በመሽሎክሎክ ለዓመታት የተንከራተተ ያልተሳካለት አርበኛ አስመስሏታል፡፡ወደ ውበት ሳሎን ጎራ ካለች ወራቶች እንዳለፏት ለሰከንድ ብቻ ሁኔታዋን በማየት ማወቅ ይቻላል ፤ በሜካፕ ያሸበርቅ የነበረው ፊቷ ወይቧል፡፡
በአንድ እጁ አቅፎ ጉንጮቾን እየሳመ‹‹ሃይ.. የውብ ሰላም ነሽ?››አላት ::
‹‹አለው..ይመስገነው…ተቀመጥ፡፡››
ከጎኗ ተቀመጠ::
‹‹እሺ...ትንግርት ሰላም ነች?››
‹‹ሰላም ነች::››
‹‹ስራዎቿን አልፎ አልፎ ጋዜጣችሁ ላይ አነባለሁ፤እንዴት ነው አላረገዘችም እንዴ?››
‹‹አላረገዘችም፡፡››
‹‹አይ ይደርሳል፤ውጭ ትቆያለህ እንዴ?››
‹‹አዎ ትንሽ ስለምቆይ እኮ ነው ሳልሰናበትሽ መሄድ ያልፈለኩት::››
‹‹አይ ጥሩ አደረግክ ፡፡››አለችው በበረደ ስሜት::
ሁኔታዎን ሲያይ ምኗም አላማረው‹‹የውብ .ጤናሽን ሰላም ነሽ ግን?››
‹‹እኔ እንጃ ባክህ..አዎ ሰላም ነኝ መሰለኝ፡፡››ያለችበት ሁኔታ ለራሷም የተምታታባት እንደሆነ በቀላሉ ተረዳ::
‹‹እንዴት እንዴት ነው...?ችግር ካለ ንገሪኝ?››
‹‹ችግር ካለ አልክ..!!!ምን ብነግርህ ምን ይገባሀል?የቱንስ ነግሬህ የቱን እተወዋለው?
እቤቱ በሙሉ ችግር በችግር ሆኗል፡፡ ሲያመጣው ደራርቦ አይደል..?››
ሁሴን ገና እንደገባ ነበር የውብዳር ጥሩ ሁኔታ ላይ እንዳልሆነች ያወቀው <<የውብ ግዴለሽም በቅደም ተከተል ዋና ዋናውን ንገሪኝ::››
‹‹እሱማ ውሎ ያሳድረናል፤ያ ደግሞ ከመንገድህ ቀረህ ማለት ነው፡፡››
‹‹አትቀልጂ ..መስማት እፈልጋለው፡፡ ንገሪኝ፡፡››
‹‹አይ ጓደኛዬ... እኔና ቀልድ ከተቆራረጥን እኮ ሰነባበትን፡፡››እንባዋ ከቁጥጥሯ ውጭ በሆነ ኃይል እስገዳጅነት ዝርግፍ አለ፡፡ሁሴን ተረበሸ፡፡የውብ ዳር እንዲህ ስትሆን አይቶ አያውቅም፡፡
እንደምንም ተረጋጋችና መናገር ጀመረች‹‹በቃ ኑሮ ሁሉ ዝብርቅርቅ ብሎብኛል፡፡ሰው ያልሰራውን ምን አይነት ክፉ ሀጥያት እንደሰራው አላውቅም?››
‹‹የምን ሀጥያት ነው፡፡እንደማንኛውም ሰው የሆነ ስህተት ሰራሽ አከተመ ፡፡እራስሽንማ በትናንት ስህተት ላይ አጣብቀሽ አትጨናነቂ፡፡ ህይወት ትቀጥላለች፡፡ ሁሉን ነገር እንደ አዲስ ጀምሪ፡፡››
‹‹እንደምትለው ቀላል አይደለም፡፡ጓደኛህ ከወንድ ጋር ስትቀብጥ አየኋት ብሎ ቤቱን ጥሎ ከወጣ በኃላ ሁሉ ነገር ብልሽትሽት
ብሎብኛል፡፡ይገርምሀል ከልጁ ጋር ፍቅር ስጀምር ተሳስቼ አልነበረም፤አውቄና አቅጄበት ነበር፡፡እሱ እኔን አሰልሎ መረጃ ከማግኘቱ
በፊት እኔ ቢያንስ ከአምስት ሴቶች በላይ ጋር ሲማግጥ በተለያየ ጊዜ ማረጋገጥ ችዬ ነበር፡፡
በወቅቱ እሱ እንዳደረገው
አላደረግኩም፡፡.ፍቅራችን ቢያበቃለትም ትዳራችን እንዲፈረካከስ ስላልፈለኩ ዝም ነበር ያልኩት፡፡እንዲህ አድርገሀል እንኳን ብዬ
ጠይቄው አላውቅም ፣ምክንያቱም እንዲበረግግ ስልፈለኩም፡፡ግን ደግሞ ሰው ነኝ ፤በምግብ ብቻ አልኖርም፡፡ስለዚህ እሱ
ሚያደርገውን በጥቂቱ ለማድረግ ተንቀሳቀስኩ፡፡ቀልቤ ያረፈበትን አንድ ሰው አፈቀርኩ፡፡ያንን ፍቅር እሱ ሲደርስበት ሁለት ወር እንኳን አላጣጠምኩትም ነበር፡፡በቃ ይሄው ነው የእኔ ሀጥያት፡፡››
‹‹በግልፅ ልጠይቅሽ፡፡ቆይ እንዳልሽው መሆን የሌለበት ሆኖ ከሰሎሞን ጋር ከተፋታችሁ በኃላ ከዛ ከልጁ ጋር እንደቀጠልሽ እርግጠኛ ነኝ፡፡››
አቋረጠችው <<አንድ ሳምንት እንኳን አብሮኝ ሊዘልቅ አልደፈረም፡፡ባልሽ ሀብታም ስለሆነ ገዳይ የሚገዛበት በቂ ብር አለው፤ቢያስገድለኝስ›› ብሎ ጥሎኝ ጠፋ፡፡
‹‹ይገርማል››አለ ሁሴን የሚለው ጠፍቶት‹‹... ግን ሰሎሞን አስፈራርቶት ነበር እንዴ?››
‹‹አይመስለኝም ..ግን አንድ ሁለት ቀን መንገድ ላይ ሲገናኙ ገለማምጦታል መሰለኝ፤ለማንኛውም ትዳሬንም ፍቅሬንም ተነጠቅኩ፡፡ይሄስ ይሁን
እቋቋመዋለው፤የልጆቼን ጥያቄ እና ጭቅጭቅ ግን እንዴት ልቻለው?››
<<ማለት?>>
ለጠየቃት ጥያቄ መልስ ከመስጠቷ በፊት ሰራተኛዋ ከልጆቹ መኝታ ቤት ወጥታ ወደ እነሱ ቀረበችና‹‹ እትዬ ተነስተዋል፡፡››አለቻት፡፡
‹‹ተነሱ?›› አለችና ከመቀመጫዋ በርግጋ ተነሳች፡፡
‹‹ምነው..?ችግር አለ እንዴ?
‹‹ልጆቹ ትንሽ አሟቸዋል›› ብላ ወደ መኝታ ቤቱ በፍጥነት መራመድ ጀመረች፡፡ ተከተላት፡፡
መኝታ ቤት እንደገቡ ሁለቱም መንታዎች አንድ አልጋ ላይ ጎን ለጎን ተኝተዋል..‹‹ምን ሆነው ነው?››በድጋሚ ጠየቀ ሁሴን ፡፡
‹‹ባክህ ማታ ነው የጀመራቸው፡፡በጣም ያተኩሳሉ፡፡ጥዋት ሀኪም ቤት ወስጄያቸው
ነበር ፤መድሀኒት ተሰጥቶቸዋል፡፡እኔ እኮ ግራ ገባኝ..… እሱ ከዚህ ቤት ከወጣ በኃላ ቢያንስ በሳምንት ሶስት ቀን ይታመማሉ››ዳግመኛ እንባዎን ዘረገፈች ፡፡ሁሴን ወደ ልጆቹ ተጠጋና እጆቹን ጭንቅላታቸው ላይ ጭኖ ሙቀታቸውን ተመለከተ፡፡ያተኩሳሉ፡፡ጠይም ፊታቸው ቸፍ ብሎ በላብ ተጠምቋል፡፡
አንደኛዋን‹‹ዕፀ‐ህይወት ምንሽን ነው የሚያምሽ ?›› ብሎ ጠየቃት፡፡
እጇን ወደ ጭንቅላቷ በመጠቆም አሳየችው፡፡
‹‹አንቺስ ምንሽን ነው የሚያምሽ?››ሌለኛውን ጠየቃት፡፡
ግራ ገባው‹‹የሚያምሽን ቦታ እኮ ነው የጠየቅኩሽ ?እንደ ዕፀ‐ህይወት እራስሽን ነው ያመመሽ?››ጥያቄው ያልገባት መስሎት አብራራላት፡፡
‹‹አይደለም፡፡አባቴን ነው የሚያመኝ፡፡አባቴን እፈልጋለሁ››አለችው፡፡ በድንጋጤ ልቡ ቀጥ ልትል ትንሽ ነበር የቀራት ፡፡አይኖቹን ወደ የውብዳር አሽከረከረ፡፡በፀጥታ እያለቀሰች ነው፡፡
‹‹ዕፀ-ህይወትም መናገር ጀመረች‹‹እኔም አባቴን ነው የሚያመኝ›› በማለት የቀድሞ መልሷን አስተካከለች፡፡
‹‹የውብ አንዴ ላናግርሽ?›› ብሎ ይዞት ወጣ፡፡
<<ምነው?>>
‹‹እንቢ እንዳትይኝ...ይዤያቸው ልውጣና ትንሽ ላዝናናቸው፡፡እርግጠኛ ነኝ ይሻላቸዋል፡፡›› አላት፡፡
እንደማሰብ አለችና ‹‹እንዳልክ፤ልብስ ልቀይርላቸው ፡፡››ብላ ተመለሰች፡፡
ከአስር ደቂቃ በኋላ ሰባት አመት ዕድሜ ያላቸውን መንትዬቹን ይዟቸው ከግቢ ወጣ፡፡
ወደ ኤድናሞል ጉዞ ጀመረ፡፡
መንገድ ላይ ሞባይሉን አወጣና ሰሎሞን ጋር ደወለ‹‹እሺ ሰላም ነህ?››
‹‹ምንም ሰላም አይደለሁ..በአስቸኳይ ኤድናሞል ና፡፡››
‹‹ምነው? ችግር አለ እንዴ?››
‹‹ስትመጣ ነግርሀለው…ከአስራ አምስት ደቂቃ
በኃላ እዛ እንገናኝ፡፡››ብሎት ስልኩን ዘጋና መኪናውን በትኩረት ማሽከርከር ጀመረ፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሁሴን ወደ ሲዊዘርላንድ ሊበር ከ3ዐ ሰዓት ያነሰ ጊዜ ቢቀረውም ከመሄዱ በፊት የውብዳርን እና ልጆቹን መሰናበት ስለፈለገ ወደ እነሱ እየሄደ ነው፡፡ ትናንትና የሽኝት ዝግጅቱ ላይ ልጆቹን ይዛ እንድትገኝ በስልክ ደውሎ ነግሯት ነበር፤እሷም እንደምትገኝ ቃሏን ስጥታው ነበር፤ነገር ግን አልተገኘችም፡፡ ያው ከድሮ ባሏ እና ከጣውንቷ ጋር ፊት ለፊት ተገናኝቶ መፍጠጥ ደብሯት እንደሆነ ስለገባው ባለመምጣቷ ብዙም ቅር አላለውም፡፡
እንደውም በተቀራኒው ከስልክ ግንኙነት ውጭ በአካል ሳያገኛት አራት ወራቶች በማሳለፉ ፀፀት ነገር ሽው ብሎበታል፡፡
ዛሬም እንደሚመጣ ሲደውልላት ቀዝቀዝ ባለ ስሜት ነበር ‹‹..በቃ ና... ቤት ነኝ፡፡››ያለችው፡፡
ደርሶ የመኪናውን ክላክስ ሲያስጮህ ዘበኛው የውጪን በራፍ ከፈተለት፡፡ መኪናውን ወደ ግቢ ውስጥ አስገባና ምቹ ቦታ ፈልጐ በማቆም ሞተሩን አጥፍቶ ወደ ውስጥ ገባ፡፡የውብዳር ሳሎን ብቻዋን ቁጭ ብላ ነበር፡፡
ሲያያት ደነገጠ.፡፡ጉስቁልቁል ብላለች፡፡የሆነ ጭምድድ ያለ ቢጃማ ቀሚስ ለብሳለች፣የፀጉሯ መንጨፍረር በየጫካው በመሽሎክሎክ ለዓመታት የተንከራተተ ያልተሳካለት አርበኛ አስመስሏታል፡፡ወደ ውበት ሳሎን ጎራ ካለች ወራቶች እንዳለፏት ለሰከንድ ብቻ ሁኔታዋን በማየት ማወቅ ይቻላል ፤ በሜካፕ ያሸበርቅ የነበረው ፊቷ ወይቧል፡፡
በአንድ እጁ አቅፎ ጉንጮቾን እየሳመ‹‹ሃይ.. የውብ ሰላም ነሽ?››አላት ::
‹‹አለው..ይመስገነው…ተቀመጥ፡፡››
ከጎኗ ተቀመጠ::
‹‹እሺ...ትንግርት ሰላም ነች?››
‹‹ሰላም ነች::››
‹‹ስራዎቿን አልፎ አልፎ ጋዜጣችሁ ላይ አነባለሁ፤እንዴት ነው አላረገዘችም እንዴ?››
‹‹አላረገዘችም፡፡››
‹‹አይ ይደርሳል፤ውጭ ትቆያለህ እንዴ?››
‹‹አዎ ትንሽ ስለምቆይ እኮ ነው ሳልሰናበትሽ መሄድ ያልፈለኩት::››
‹‹አይ ጥሩ አደረግክ ፡፡››አለችው በበረደ ስሜት::
ሁኔታዎን ሲያይ ምኗም አላማረው‹‹የውብ .ጤናሽን ሰላም ነሽ ግን?››
‹‹እኔ እንጃ ባክህ..አዎ ሰላም ነኝ መሰለኝ፡፡››ያለችበት ሁኔታ ለራሷም የተምታታባት እንደሆነ በቀላሉ ተረዳ::
‹‹እንዴት እንዴት ነው...?ችግር ካለ ንገሪኝ?››
‹‹ችግር ካለ አልክ..!!!ምን ብነግርህ ምን ይገባሀል?የቱንስ ነግሬህ የቱን እተወዋለው?
እቤቱ በሙሉ ችግር በችግር ሆኗል፡፡ ሲያመጣው ደራርቦ አይደል..?››
ሁሴን ገና እንደገባ ነበር የውብዳር ጥሩ ሁኔታ ላይ እንዳልሆነች ያወቀው <<የውብ ግዴለሽም በቅደም ተከተል ዋና ዋናውን ንገሪኝ::››
‹‹እሱማ ውሎ ያሳድረናል፤ያ ደግሞ ከመንገድህ ቀረህ ማለት ነው፡፡››
‹‹አትቀልጂ ..መስማት እፈልጋለው፡፡ ንገሪኝ፡፡››
‹‹አይ ጓደኛዬ... እኔና ቀልድ ከተቆራረጥን እኮ ሰነባበትን፡፡››እንባዋ ከቁጥጥሯ ውጭ በሆነ ኃይል እስገዳጅነት ዝርግፍ አለ፡፡ሁሴን ተረበሸ፡፡የውብ ዳር እንዲህ ስትሆን አይቶ አያውቅም፡፡
እንደምንም ተረጋጋችና መናገር ጀመረች‹‹በቃ ኑሮ ሁሉ ዝብርቅርቅ ብሎብኛል፡፡ሰው ያልሰራውን ምን አይነት ክፉ ሀጥያት እንደሰራው አላውቅም?››
‹‹የምን ሀጥያት ነው፡፡እንደማንኛውም ሰው የሆነ ስህተት ሰራሽ አከተመ ፡፡እራስሽንማ በትናንት ስህተት ላይ አጣብቀሽ አትጨናነቂ፡፡ ህይወት ትቀጥላለች፡፡ ሁሉን ነገር እንደ አዲስ ጀምሪ፡፡››
‹‹እንደምትለው ቀላል አይደለም፡፡ጓደኛህ ከወንድ ጋር ስትቀብጥ አየኋት ብሎ ቤቱን ጥሎ ከወጣ በኃላ ሁሉ ነገር ብልሽትሽት
ብሎብኛል፡፡ይገርምሀል ከልጁ ጋር ፍቅር ስጀምር ተሳስቼ አልነበረም፤አውቄና አቅጄበት ነበር፡፡እሱ እኔን አሰልሎ መረጃ ከማግኘቱ
በፊት እኔ ቢያንስ ከአምስት ሴቶች በላይ ጋር ሲማግጥ በተለያየ ጊዜ ማረጋገጥ ችዬ ነበር፡፡
በወቅቱ እሱ እንዳደረገው
አላደረግኩም፡፡.ፍቅራችን ቢያበቃለትም ትዳራችን እንዲፈረካከስ ስላልፈለኩ ዝም ነበር ያልኩት፡፡እንዲህ አድርገሀል እንኳን ብዬ
ጠይቄው አላውቅም ፣ምክንያቱም እንዲበረግግ ስልፈለኩም፡፡ግን ደግሞ ሰው ነኝ ፤በምግብ ብቻ አልኖርም፡፡ስለዚህ እሱ
ሚያደርገውን በጥቂቱ ለማድረግ ተንቀሳቀስኩ፡፡ቀልቤ ያረፈበትን አንድ ሰው አፈቀርኩ፡፡ያንን ፍቅር እሱ ሲደርስበት ሁለት ወር እንኳን አላጣጠምኩትም ነበር፡፡በቃ ይሄው ነው የእኔ ሀጥያት፡፡››
‹‹በግልፅ ልጠይቅሽ፡፡ቆይ እንዳልሽው መሆን የሌለበት ሆኖ ከሰሎሞን ጋር ከተፋታችሁ በኃላ ከዛ ከልጁ ጋር እንደቀጠልሽ እርግጠኛ ነኝ፡፡››
አቋረጠችው <<አንድ ሳምንት እንኳን አብሮኝ ሊዘልቅ አልደፈረም፡፡ባልሽ ሀብታም ስለሆነ ገዳይ የሚገዛበት በቂ ብር አለው፤ቢያስገድለኝስ›› ብሎ ጥሎኝ ጠፋ፡፡
‹‹ይገርማል››አለ ሁሴን የሚለው ጠፍቶት‹‹... ግን ሰሎሞን አስፈራርቶት ነበር እንዴ?››
‹‹አይመስለኝም ..ግን አንድ ሁለት ቀን መንገድ ላይ ሲገናኙ ገለማምጦታል መሰለኝ፤ለማንኛውም ትዳሬንም ፍቅሬንም ተነጠቅኩ፡፡ይሄስ ይሁን
እቋቋመዋለው፤የልጆቼን ጥያቄ እና ጭቅጭቅ ግን እንዴት ልቻለው?››
<<ማለት?>>
ለጠየቃት ጥያቄ መልስ ከመስጠቷ በፊት ሰራተኛዋ ከልጆቹ መኝታ ቤት ወጥታ ወደ እነሱ ቀረበችና‹‹ እትዬ ተነስተዋል፡፡››አለቻት፡፡
‹‹ተነሱ?›› አለችና ከመቀመጫዋ በርግጋ ተነሳች፡፡
‹‹ምነው..?ችግር አለ እንዴ?
‹‹ልጆቹ ትንሽ አሟቸዋል›› ብላ ወደ መኝታ ቤቱ በፍጥነት መራመድ ጀመረች፡፡ ተከተላት፡፡
መኝታ ቤት እንደገቡ ሁለቱም መንታዎች አንድ አልጋ ላይ ጎን ለጎን ተኝተዋል..‹‹ምን ሆነው ነው?››በድጋሚ ጠየቀ ሁሴን ፡፡
‹‹ባክህ ማታ ነው የጀመራቸው፡፡በጣም ያተኩሳሉ፡፡ጥዋት ሀኪም ቤት ወስጄያቸው
ነበር ፤መድሀኒት ተሰጥቶቸዋል፡፡እኔ እኮ ግራ ገባኝ..… እሱ ከዚህ ቤት ከወጣ በኃላ ቢያንስ በሳምንት ሶስት ቀን ይታመማሉ››ዳግመኛ እንባዎን ዘረገፈች ፡፡ሁሴን ወደ ልጆቹ ተጠጋና እጆቹን ጭንቅላታቸው ላይ ጭኖ ሙቀታቸውን ተመለከተ፡፡ያተኩሳሉ፡፡ጠይም ፊታቸው ቸፍ ብሎ በላብ ተጠምቋል፡፡
አንደኛዋን‹‹ዕፀ‐ህይወት ምንሽን ነው የሚያምሽ ?›› ብሎ ጠየቃት፡፡
እጇን ወደ ጭንቅላቷ በመጠቆም አሳየችው፡፡
‹‹አንቺስ ምንሽን ነው የሚያምሽ?››ሌለኛውን ጠየቃት፡፡
ግራ ገባው‹‹የሚያምሽን ቦታ እኮ ነው የጠየቅኩሽ ?እንደ ዕፀ‐ህይወት እራስሽን ነው ያመመሽ?››ጥያቄው ያልገባት መስሎት አብራራላት፡፡
‹‹አይደለም፡፡አባቴን ነው የሚያመኝ፡፡አባቴን እፈልጋለሁ››አለችው፡፡ በድንጋጤ ልቡ ቀጥ ልትል ትንሽ ነበር የቀራት ፡፡አይኖቹን ወደ የውብዳር አሽከረከረ፡፡በፀጥታ እያለቀሰች ነው፡፡
‹‹ዕፀ-ህይወትም መናገር ጀመረች‹‹እኔም አባቴን ነው የሚያመኝ›› በማለት የቀድሞ መልሷን አስተካከለች፡፡
‹‹የውብ አንዴ ላናግርሽ?›› ብሎ ይዞት ወጣ፡፡
<<ምነው?>>
‹‹እንቢ እንዳትይኝ...ይዤያቸው ልውጣና ትንሽ ላዝናናቸው፡፡እርግጠኛ ነኝ ይሻላቸዋል፡፡›› አላት፡፡
እንደማሰብ አለችና ‹‹እንዳልክ፤ልብስ ልቀይርላቸው ፡፡››ብላ ተመለሰች፡፡
ከአስር ደቂቃ በኋላ ሰባት አመት ዕድሜ ያላቸውን መንትዬቹን ይዟቸው ከግቢ ወጣ፡፡
ወደ ኤድናሞል ጉዞ ጀመረ፡፡
መንገድ ላይ ሞባይሉን አወጣና ሰሎሞን ጋር ደወለ‹‹እሺ ሰላም ነህ?››
‹‹ምንም ሰላም አይደለሁ..በአስቸኳይ ኤድናሞል ና፡፡››
‹‹ምነው? ችግር አለ እንዴ?››
‹‹ስትመጣ ነግርሀለው…ከአስራ አምስት ደቂቃ
በኃላ እዛ እንገናኝ፡፡››ብሎት ስልኩን ዘጋና መኪናውን በትኩረት ማሽከርከር ጀመረ፡፡
👍88❤8👏2😁1
ልጆቹን ከአባታቸው ጋር አገናኝቶ ለጊዜውም
ቢሆን እንዲሻላቸው ማድረግ፤በዘላቂነትም
መሆን ያለበትን ነገር ከአባትዬውም ሆነ
ከኤደን ጋር ተነጋግሮ ሁኔታዎችን ለማስተካከል
አቀደ፡፡..ቢያንስ የቅዳሜና የእሁድ የእረፍት ቀናቸውን አባታቸው ጋር ማሰለፍ እንዳለባቸውና ይሄንንም ማስተካከል የእሱ ኃላፊነት እንደሆነ ወሰነ፡፡
✨ይቀጥላል✨
አሁንም ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ አበረታቱን ቤተሰቦች
ሰብስክረይብ ያላደረጋችሁ በማድረግ ….ያደረጋችሁ ደግሞ ሌሎች እዲያደርጉ በማስተባበር ተባበሩኝ… አመሰግናለሁ፡፡
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ቢሆን እንዲሻላቸው ማድረግ፤በዘላቂነትም
መሆን ያለበትን ነገር ከአባትዬውም ሆነ
ከኤደን ጋር ተነጋግሮ ሁኔታዎችን ለማስተካከል
አቀደ፡፡..ቢያንስ የቅዳሜና የእሁድ የእረፍት ቀናቸውን አባታቸው ጋር ማሰለፍ እንዳለባቸውና ይሄንንም ማስተካከል የእሱ ኃላፊነት እንደሆነ ወሰነ፡፡
✨ይቀጥላል✨
አሁንም ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ አበረታቱን ቤተሰቦች
ሰብስክረይብ ያላደረጋችሁ በማድረግ ….ያደረጋችሁ ደግሞ ሌሎች እዲያደርጉ በማስተባበር ተባበሩኝ… አመሰግናለሁ፡፡
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍67❤8😢4
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሀዋሳ
ሁሴን ወደ ሲዩዘርላንድ ከበረረ ሀያ ቀን አልፎታል፡፡ያለፉትን ሀያ ቀናት የእሱንም ቦታ ተክታ ለስራው ከላይ እታች በመሯሯጥ ብታሳልፍም ከናፍቆት ግን ማምለጥ አልቻለችም፡፡አዎ ሁሴን ባልተለመደ መልኩ በጣም ናፍቋታል፡፡እራሷን በሌላ ሰው ህልውና ላይ ይሄን ያህል መለጠፍ አትፈልግም ነበር፤ምንም ቋሚና ዘላቂ ነገር እንደሌለ ህይወት ደጋግማ አስተምራታለች፡፡የእኔ የምትለው ነገር ሁሉ አንድ ቀን በሰላምም ሆነ በአደጋ ብቻ በሆነ ምክንያት እንደሚለያትና ለዛም ዝግጁ ሆና መጠበቅ እንዳለባት የዘወትር መፈክሯና መመሪያዋ ነበር፡፡አሁን ግን መልሳ ደከመች፤እናም ባሏ ናፈቃት፡፡እለቱ ሰንበት ስለሆነ የቤቷ ሳሎን ሶፋ ላይ ጋደም ብላ ቴሌቪዢን እየተመለከተች ነው፡፡
አይድል ፕሮግራም..በሀዋሳ የሚካሄድ የማጣሪያ ውድድር እየተመለከተች ነው፡፡
በአብረሀም ወልዴ የሚመራው የዳኞች ቡድን
የዳኝነት ቦታቸውን ይዘዋል፡፡ተወዳዳሪዎች በቅደም ተከተል ወደ መድረክ እየወጡ የተዘጋጁበትን ዘፈን በመዝፈን ተፈጥሮ
የቸረቻቸውን ድምጽና በጥረታቸው ያደበሩትን
ችሎታ በማዋሀድ ዳኞቹንም ሆነ ተመልካቾችን
በማሳመን ለአዲስአበባው ውድድር ለማለፍ ይጥራሉ፡፡ጥቂቶች ይሳካላቸዋል ፤ሌሎቹ ደግሞ አንገት ደፍተውና ፈዘው ከመድረኩ
ይሰናበታሉ፡፡ትንግርት ሁሌ ይህን ፕሮግራም ስታይ ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ነው የሚሰማት፡፡
ዘና የሚያደርገት እንዳለ ሁሉ የሚያሳዝኗትም
ተወዳዳሪዎች አሉ፡፡ከችሎታቸው በላይ
ጉጉታቸው የናረ፣ብዙ ተስፋ አድርገው መጥተው በዳኞቹ ቁርጥ ያለ ሞያዊ
አስተያየት ሽምቅቅ የሚሉ ወጣት ጨቅላዎች፤ ያሳዝኗታል፡፡ችሎታው እያላቸውም ፍራቻቸውን ብቻ ማሸነፍ ተስኗቸው ያላቸውን ነገር መግለጽ ባለመቻላቸው አጉል የሚሆኑም አሉ፤እነሱም ያሳዝኗታል፡፡
...አሁን ግን እያየች ያለቻው ድንቅና የሚያስደምም ችሎታ ነው፡፡አስር ሁለት አመት የማይበልጣቸው ሁለት ሴት ልጆች ናቸው የሚታዩት፡፡አንደኛዋ ጊታሯን ይዛ የተዘጋጀላት መቀመጫ ላይ ተቀመጠችና በጣቶቿ የጊታሩን ክሮች በመነካካት ፈታተሸች፤ሌለኛዋ ከፊት ለፊቷ በሜትሮች ርቀት ማይኩን ይዛ ::
አብረሀም ወልዴ መናገር ጀመረ....
‹‹እሺ እንኳን በሰላም መጣችሁ እያልኩ እራሳችሁን እንድታስተዋውቁ ዕድሉን ልስጣችሁ ፡፡››
‹‹ስሜ ሀሊማ ታዲዬስ ይባላል፡፡ የምጫወትላችሁ የተፈራ ካሳን ‹አባብዬ› የሚለውን ዘፈን ነው፡፡››
‹‹አሪፍ ነው፡፡ባለጊታሯስ ስምሽ ማነው ?››
‹‹ስሜ ሄለን ታዲዬስ ይባላል፤ጊታርና ፒያኖ ተጨዋች ነኝ።
<<እህት አማቾች ናችሁ ?››አረጋኸኝ መሀከል ገብቶ ጠየቀ፡፡
‹‹አዎ እህቴ ናት፡፡››
ይሄ ሁሉ ሲሆን ትንግርት ስትከታተል የነበረው በግማሽ ልቧ ነበር፡፡እህትማማቾች ነን ሲሉ ግን ትንሽ ግር አላት፡፡በእኩል ዕድሜ ላይ ናቸው፡፡የትኛዋ ታላቅ የትኛዋ ደግሞ ታናሽ ትሆን? ስትል እራሷን ጥያቄ ጠየቀች፡፡ ደግሞ ምናቸውም አይመሳሰልም <<የእናት ሆድ ዥንጉርጉር›› ይባል የለ ብላ ለራሷ መልስ ሰጠች፡፡
‹‹በሉ ቀጥሉ..መልካም ዕድል፡፡››ከዳኞቹ ፍቃድ አገኙ፡፡
ሄለን እነዛ ቀጫጭንና ለጋ ጣቶቾን የጊታሩ ክሮች ላይ ማርመስመስ ጀመረች ፡፡ የሙዚቃ መሳሪያውን ምት ተከትሎ የሀሊማ ተስረቅራቂና ማራኪ ድምጽ ይንቆረቆር ጀመር፡፡ በአዳራሹ የሞላው ተመልካች ብቻ ሳይሆን በየቤቱ በቲቪ ፕሮግራሙን የሚከታተለው ህዝብም ፀጥ የሚያሰኝ አደንዛዥ ድምጽ ነበር፡፡በዚህ ዕድሜ በእንዲህ አይነት ችሎታ? እንዴት ነው በዚህ ዕድሜ የሙዚቃ መሳሪያን ስልተ-ምት ጠብቆ ስይደናገሩና ሳይንሸራተቱ በዚህ ልክ መዝፈን የቻሉት?፡፡
ዳኞቹ ሳይቀር አፋቸውን ከፈቱ፡፡ደግሞ በሙዚቃው ሁለቱም ጉንጮች ላይ እንባ እየተንጠባጠበ ነው፡፡ሲጨርሱ የአዳራሹ ሰው ሁሉ አረንጎዴ ካርዱን እያወዛወዘ ከመቀመጨው ተነሳ፡፡ደኞቹም እያጨበጨቡ ቆሙ .. መድረክ ድረስ በመሄድ በየተራ አቅፈው ሳሟቸው፡፡
አስተያየት መስጠት ተጀመረ..የመጀመሪያው ዳኛ
‹‹በእውነት ሀዋሳ እናንተን የመሰሉ ባለድንቅ ችሎታ ሙዚቀኞችን ስላፈራች እድለኛ ነች፡፡
እኛም እዚህ መጥተን እናንተን ስላገኘን እድለኞች ነን፤በቃ ልዩ ናችሁ፡፡››
ሁለተኛው ዳኛ…..
‹‹ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ሙዚቃው ከህይወታችሁ ጋር የሚያይዘው ጉዳይ አለ? ሁለታችሁም ስታለቅሱ ነበር፡፡እኔንም አስለቅሳችሁኛል፡፡ምከንያት ነበራችሁ?››
ሀሊማ መናገር ጀመረች‹‹አዎ ሁለታቸንም አባታችንን በጣም እንወደዋለን፡፡እርግጥ ሁሉም ሰው አባቱን በጣም ይወዳል፡፡እመኑን የእኛ አባት ግን ልዩ ሰው ነው፡፡›› አዳራሹ በሳቅና በጭብጨባ ተናጋ፡፡
ሄለን ቀጠለች‹‹ታዲያ አንተ አባታችን ባትሆን ኖሮ እኛ ዛሬ እንዲህ አምሮብን ሙዚቃ እየተጫወትን እንዲህ አዳራሽ ሙሉ ህዝብ እያጨበጨበልን አንታይም ነበር.፡፡ምክንያም እድሉም ጊዜውም አይኖረንም ነበር፡፡አዎ አባት ባትሆነን ኖሮ ይሄኔ ሁለታችንም አሞራ ገደል
አካባቢ ከሚገኝ ቆሻሻ መጣያ ገንዳ ውስጥ ተበላሽቶ የተጣለ ምግብ ከቆሻሻው በመለየት በመመገብ ላይ ነበርን፡፡…እና ከእንደገና ስለፈጠርከን አመሰግናለሁ ...ታዲ እንወድሀለን፡፡››
ዳኞቹም ታዳሚዎቹም ከልጆቹ ችሎታ በላይ በንግግራቸው ድንግርግር እንዳሉ ፊታቸውን በመመልከት ማወቅ ይቻላል፡፡
‹‹እባክህ አቶ ታዲዬስ እዚህ አዳራሽ ውስጥ ካላህ ወደ መድረክ ወጥተህ አንድ ነገር በለን››ከዳኞቹ መካከል አንድ ተናገረ፡፡ በአዳራሹ ያላው ታዳሚ እርስ በርሱ ዞር ዞር በማለት መተያየት ጀመረ፡፡ከመቀመጫው ተነስቶ ወደ መድረክ የሚወጣ ሰው ለመመልከት፡፡
‹‹ታዲ ና እንጂ››ሄለን ከመድረክ ተማፀነች፡፡
የሁለት ልጆች አባት ሳይሆን ተደባበዳቢ ቦዴ ጋርድ የሚመስል ጠይም ደንዳና ወጣት ወደ መድረኩ ወጣና ሁለቱንም ልጆቹን አቅፎ
ጉንጮቻቸውን ከሳመ በኃላ ማይኩን ተቀብሎ መናገር ጀመረ፡፡‹‹ታዴዬስ ማለት እኔ ነኝ፡፡ልጆቼ
ስለእኔ ያሉት ትንሽ ተጋኗል፡፡እውነታው በተቃራኒው ነው፡፡እነሱ ልጆቼ በመሆናቸው
በአሁኑ ወቅት በአለም በጣም እድለኛው ሰው
እኔ ነኝ፡፡ምን አልባት ችሎታቸውን አይታችሁ
ስታጨበጭቡላቸው ነበር፡፡ግን እመኑኝ መድረክ የመጀመሪያ ቀናቸው ስለሆነ የችሎታቸውን ግማሽም አላሳዮችሁም...እናም
ሁላችሁም እዚህ አዳራሹን የሞላችሁ ሁሉ ብትቀኑብኝ አይገርመኝም፡፡ምክንያቱም እኔ የእነዚህ ዕንቁ ልጆች አባት ነኝ፡፡አመሰግናለሁ፡፡>> ብሎ ወረደ፡፡ፕሮግራሙ ቢያልቅም ትንግርት
ስለልጆቹም ሆነ ስለአባትዬው ልትረሳ
አልቻለችም፡፡የሆነ ያልተለመደ ነገር ነው
የሆነባት፡፡<<አባታችን ባትሆን የቆሻሻ ገንዳ ላይ
ምግብ እንለቃቅም ነበር›› ሲሉ ምን ማለታቸው ነው?ግን የእውነት አባታቸው ነው ?
አልመሰላትም፡፡እንዴት አድርጎ ቢያሳድጋቸው
ነው በዚህ መጠን ሊወዱት የቻሉት?እውነትም
እሱ እንዳለው የሚቀናበት አባት ነው ? አለችና ቲቪውን አጥፍታ አየር ለመቀበል ቤቷን ለቃ ወደ ውጭ ወጣች፡፡
✨ይቀጥላል✨
አሁንም ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ አበረታቱን ቤተሰቦች እያደረጋቹ አደለም በየቀኑ ለመልቀቅ እየሞከርኩ ነው እናንተም ማበረታታችሁን ቀጥሉ አመሰጎናለሁ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ሀዋሳ
ሁሴን ወደ ሲዩዘርላንድ ከበረረ ሀያ ቀን አልፎታል፡፡ያለፉትን ሀያ ቀናት የእሱንም ቦታ ተክታ ለስራው ከላይ እታች በመሯሯጥ ብታሳልፍም ከናፍቆት ግን ማምለጥ አልቻለችም፡፡አዎ ሁሴን ባልተለመደ መልኩ በጣም ናፍቋታል፡፡እራሷን በሌላ ሰው ህልውና ላይ ይሄን ያህል መለጠፍ አትፈልግም ነበር፤ምንም ቋሚና ዘላቂ ነገር እንደሌለ ህይወት ደጋግማ አስተምራታለች፡፡የእኔ የምትለው ነገር ሁሉ አንድ ቀን በሰላምም ሆነ በአደጋ ብቻ በሆነ ምክንያት እንደሚለያትና ለዛም ዝግጁ ሆና መጠበቅ እንዳለባት የዘወትር መፈክሯና መመሪያዋ ነበር፡፡አሁን ግን መልሳ ደከመች፤እናም ባሏ ናፈቃት፡፡እለቱ ሰንበት ስለሆነ የቤቷ ሳሎን ሶፋ ላይ ጋደም ብላ ቴሌቪዢን እየተመለከተች ነው፡፡
አይድል ፕሮግራም..በሀዋሳ የሚካሄድ የማጣሪያ ውድድር እየተመለከተች ነው፡፡
በአብረሀም ወልዴ የሚመራው የዳኞች ቡድን
የዳኝነት ቦታቸውን ይዘዋል፡፡ተወዳዳሪዎች በቅደም ተከተል ወደ መድረክ እየወጡ የተዘጋጁበትን ዘፈን በመዝፈን ተፈጥሮ
የቸረቻቸውን ድምጽና በጥረታቸው ያደበሩትን
ችሎታ በማዋሀድ ዳኞቹንም ሆነ ተመልካቾችን
በማሳመን ለአዲስአበባው ውድድር ለማለፍ ይጥራሉ፡፡ጥቂቶች ይሳካላቸዋል ፤ሌሎቹ ደግሞ አንገት ደፍተውና ፈዘው ከመድረኩ
ይሰናበታሉ፡፡ትንግርት ሁሌ ይህን ፕሮግራም ስታይ ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ነው የሚሰማት፡፡
ዘና የሚያደርገት እንዳለ ሁሉ የሚያሳዝኗትም
ተወዳዳሪዎች አሉ፡፡ከችሎታቸው በላይ
ጉጉታቸው የናረ፣ብዙ ተስፋ አድርገው መጥተው በዳኞቹ ቁርጥ ያለ ሞያዊ
አስተያየት ሽምቅቅ የሚሉ ወጣት ጨቅላዎች፤ ያሳዝኗታል፡፡ችሎታው እያላቸውም ፍራቻቸውን ብቻ ማሸነፍ ተስኗቸው ያላቸውን ነገር መግለጽ ባለመቻላቸው አጉል የሚሆኑም አሉ፤እነሱም ያሳዝኗታል፡፡
...አሁን ግን እያየች ያለቻው ድንቅና የሚያስደምም ችሎታ ነው፡፡አስር ሁለት አመት የማይበልጣቸው ሁለት ሴት ልጆች ናቸው የሚታዩት፡፡አንደኛዋ ጊታሯን ይዛ የተዘጋጀላት መቀመጫ ላይ ተቀመጠችና በጣቶቿ የጊታሩን ክሮች በመነካካት ፈታተሸች፤ሌለኛዋ ከፊት ለፊቷ በሜትሮች ርቀት ማይኩን ይዛ ::
አብረሀም ወልዴ መናገር ጀመረ....
‹‹እሺ እንኳን በሰላም መጣችሁ እያልኩ እራሳችሁን እንድታስተዋውቁ ዕድሉን ልስጣችሁ ፡፡››
‹‹ስሜ ሀሊማ ታዲዬስ ይባላል፡፡ የምጫወትላችሁ የተፈራ ካሳን ‹አባብዬ› የሚለውን ዘፈን ነው፡፡››
‹‹አሪፍ ነው፡፡ባለጊታሯስ ስምሽ ማነው ?››
‹‹ስሜ ሄለን ታዲዬስ ይባላል፤ጊታርና ፒያኖ ተጨዋች ነኝ።
<<እህት አማቾች ናችሁ ?››አረጋኸኝ መሀከል ገብቶ ጠየቀ፡፡
‹‹አዎ እህቴ ናት፡፡››
ይሄ ሁሉ ሲሆን ትንግርት ስትከታተል የነበረው በግማሽ ልቧ ነበር፡፡እህትማማቾች ነን ሲሉ ግን ትንሽ ግር አላት፡፡በእኩል ዕድሜ ላይ ናቸው፡፡የትኛዋ ታላቅ የትኛዋ ደግሞ ታናሽ ትሆን? ስትል እራሷን ጥያቄ ጠየቀች፡፡ ደግሞ ምናቸውም አይመሳሰልም <<የእናት ሆድ ዥንጉርጉር›› ይባል የለ ብላ ለራሷ መልስ ሰጠች፡፡
‹‹በሉ ቀጥሉ..መልካም ዕድል፡፡››ከዳኞቹ ፍቃድ አገኙ፡፡
ሄለን እነዛ ቀጫጭንና ለጋ ጣቶቾን የጊታሩ ክሮች ላይ ማርመስመስ ጀመረች ፡፡ የሙዚቃ መሳሪያውን ምት ተከትሎ የሀሊማ ተስረቅራቂና ማራኪ ድምጽ ይንቆረቆር ጀመር፡፡ በአዳራሹ የሞላው ተመልካች ብቻ ሳይሆን በየቤቱ በቲቪ ፕሮግራሙን የሚከታተለው ህዝብም ፀጥ የሚያሰኝ አደንዛዥ ድምጽ ነበር፡፡በዚህ ዕድሜ በእንዲህ አይነት ችሎታ? እንዴት ነው በዚህ ዕድሜ የሙዚቃ መሳሪያን ስልተ-ምት ጠብቆ ስይደናገሩና ሳይንሸራተቱ በዚህ ልክ መዝፈን የቻሉት?፡፡
ዳኞቹ ሳይቀር አፋቸውን ከፈቱ፡፡ደግሞ በሙዚቃው ሁለቱም ጉንጮች ላይ እንባ እየተንጠባጠበ ነው፡፡ሲጨርሱ የአዳራሹ ሰው ሁሉ አረንጎዴ ካርዱን እያወዛወዘ ከመቀመጨው ተነሳ፡፡ደኞቹም እያጨበጨቡ ቆሙ .. መድረክ ድረስ በመሄድ በየተራ አቅፈው ሳሟቸው፡፡
አስተያየት መስጠት ተጀመረ..የመጀመሪያው ዳኛ
‹‹በእውነት ሀዋሳ እናንተን የመሰሉ ባለድንቅ ችሎታ ሙዚቀኞችን ስላፈራች እድለኛ ነች፡፡
እኛም እዚህ መጥተን እናንተን ስላገኘን እድለኞች ነን፤በቃ ልዩ ናችሁ፡፡››
ሁለተኛው ዳኛ…..
‹‹ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ሙዚቃው ከህይወታችሁ ጋር የሚያይዘው ጉዳይ አለ? ሁለታችሁም ስታለቅሱ ነበር፡፡እኔንም አስለቅሳችሁኛል፡፡ምከንያት ነበራችሁ?››
ሀሊማ መናገር ጀመረች‹‹አዎ ሁለታቸንም አባታችንን በጣም እንወደዋለን፡፡እርግጥ ሁሉም ሰው አባቱን በጣም ይወዳል፡፡እመኑን የእኛ አባት ግን ልዩ ሰው ነው፡፡›› አዳራሹ በሳቅና በጭብጨባ ተናጋ፡፡
ሄለን ቀጠለች‹‹ታዲያ አንተ አባታችን ባትሆን ኖሮ እኛ ዛሬ እንዲህ አምሮብን ሙዚቃ እየተጫወትን እንዲህ አዳራሽ ሙሉ ህዝብ እያጨበጨበልን አንታይም ነበር.፡፡ምክንያም እድሉም ጊዜውም አይኖረንም ነበር፡፡አዎ አባት ባትሆነን ኖሮ ይሄኔ ሁለታችንም አሞራ ገደል
አካባቢ ከሚገኝ ቆሻሻ መጣያ ገንዳ ውስጥ ተበላሽቶ የተጣለ ምግብ ከቆሻሻው በመለየት በመመገብ ላይ ነበርን፡፡…እና ከእንደገና ስለፈጠርከን አመሰግናለሁ ...ታዲ እንወድሀለን፡፡››
ዳኞቹም ታዳሚዎቹም ከልጆቹ ችሎታ በላይ በንግግራቸው ድንግርግር እንዳሉ ፊታቸውን በመመልከት ማወቅ ይቻላል፡፡
‹‹እባክህ አቶ ታዲዬስ እዚህ አዳራሽ ውስጥ ካላህ ወደ መድረክ ወጥተህ አንድ ነገር በለን››ከዳኞቹ መካከል አንድ ተናገረ፡፡ በአዳራሹ ያላው ታዳሚ እርስ በርሱ ዞር ዞር በማለት መተያየት ጀመረ፡፡ከመቀመጫው ተነስቶ ወደ መድረክ የሚወጣ ሰው ለመመልከት፡፡
‹‹ታዲ ና እንጂ››ሄለን ከመድረክ ተማፀነች፡፡
የሁለት ልጆች አባት ሳይሆን ተደባበዳቢ ቦዴ ጋርድ የሚመስል ጠይም ደንዳና ወጣት ወደ መድረኩ ወጣና ሁለቱንም ልጆቹን አቅፎ
ጉንጮቻቸውን ከሳመ በኃላ ማይኩን ተቀብሎ መናገር ጀመረ፡፡‹‹ታዴዬስ ማለት እኔ ነኝ፡፡ልጆቼ
ስለእኔ ያሉት ትንሽ ተጋኗል፡፡እውነታው በተቃራኒው ነው፡፡እነሱ ልጆቼ በመሆናቸው
በአሁኑ ወቅት በአለም በጣም እድለኛው ሰው
እኔ ነኝ፡፡ምን አልባት ችሎታቸውን አይታችሁ
ስታጨበጭቡላቸው ነበር፡፡ግን እመኑኝ መድረክ የመጀመሪያ ቀናቸው ስለሆነ የችሎታቸውን ግማሽም አላሳዮችሁም...እናም
ሁላችሁም እዚህ አዳራሹን የሞላችሁ ሁሉ ብትቀኑብኝ አይገርመኝም፡፡ምክንያቱም እኔ የእነዚህ ዕንቁ ልጆች አባት ነኝ፡፡አመሰግናለሁ፡፡>> ብሎ ወረደ፡፡ፕሮግራሙ ቢያልቅም ትንግርት
ስለልጆቹም ሆነ ስለአባትዬው ልትረሳ
አልቻለችም፡፡የሆነ ያልተለመደ ነገር ነው
የሆነባት፡፡<<አባታችን ባትሆን የቆሻሻ ገንዳ ላይ
ምግብ እንለቃቅም ነበር›› ሲሉ ምን ማለታቸው ነው?ግን የእውነት አባታቸው ነው ?
አልመሰላትም፡፡እንዴት አድርጎ ቢያሳድጋቸው
ነው በዚህ መጠን ሊወዱት የቻሉት?እውነትም
እሱ እንዳለው የሚቀናበት አባት ነው ? አለችና ቲቪውን አጥፍታ አየር ለመቀበል ቤቷን ለቃ ወደ ውጭ ወጣች፡፡
✨ይቀጥላል✨
አሁንም ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ አበረታቱን ቤተሰቦች እያደረጋቹ አደለም በየቀኑ ለመልቀቅ እየሞከርኩ ነው እናንተም ማበረታታችሁን ቀጥሉ አመሰጎናለሁ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍122❤14👏3🔥1
💥💞#አልተዘዋወረችም💥💞
✍ አሌክስ አብርሃም
ክፍል ስድስት
እስከ አሁን እዚህ ነሽ!?
ከተለያዬን ከዓመት በኋላ (በትክክል ዓመት የሞላው እንኳን አይመስለኝም)፣ አዘውትረን እንሄድበት ወደነበረው የሜክሲኮው ሬስቶራንት ሄድኩ። ለነገሩ ከዚያም በፊት ብዙ ጊዜ ሄጃለሁ፡፡ ብቻዬንም፣ ጓደኞቼም ጋር። ትዝታዬ ደብዝዞ ሌላ ትዝታ ቢጻፍበትም፣ እዚያ ቤት በሄድኩ ቁጥር ግን አስታውሳት ነበር። በተለይ እነዚያን ሳያቋርጡ ዘፈን የሚያንቆረቁሩ “ስፒከሮች” ሳይ፣ ማሂሰላምን አስታውሳት ነበር፡፡ ሳልወድ በግድ የዘፈኖቹን ግጥሞች ለማድመጥ እሞክራለሁ "ሰው ሲደሰት ዜማውን፣ ሲያዝን ግጥሙን ይሰማል" ያለው ማን ነበር!?.... የዘፈኖቹን ግጥሞች ለመያዝ አእምሮዬ ይሰንፋል፤ ያውም እኔ...ግጥም እስትንፋሴ ነው የምል እኔ። የዚያን ቀን ቤቱን ስለምወደው፣ እዚያው ሰው ቀጥሬ ነበር... ሴት ቀጥሬ። በዕድሜና በቁመት የምትበልጠኝን ሴት ቀጥሬ፡ አፏ ሥር ተለግቼ፣ ሳቋንና ወሬዋን ሰምቼ የማልጠግብላት ሴት ቀጥሬ፡፡ ስገባ ማንን አገኜሁ?...ማሂሰላምን _ ከእነባሏ...ደነገጥኩ! የእውነት ደነገጥኩ። መጀመሪያ አራት ዓመት አብራኝ የቆዬች ፍቅረኛዬን (አብሮኝ የቆዬ ጠይም ሰውነት ብል ይቀላል) የሆነ ሌላ ሰው ጋር ማዬት በራሱ ለመልመድ ጊዜ የሚወስድ የመደናገር ማዕበል ያስነሳል፡፡ ቀጥሎ ሰላም ማለት አለብኝ ወይስ የለብኝም? የሚል ጥያቄ ይከተላል....ግራ ተጋባሁ፡፡ ትንሽ ምቾት ነሳኝ- ነገሩ ...አልተነጋገርንም ሰላም አልተባባልንም፡፡ ለምን ሰላም እንዳላለችኝ ገርሞኛል፡፡ እንዲያውም እንደማታውቀኝ ዓይኗን እኔ ላይ ላለማሳረፍ ስትጥር ነበር፡፡ ይኼን ነገሯን ሳይ፣ እኔም ሰላም የማለት ዕቅዴን ተውኩትና ሩቅና ሩቅ ሆነን ተፋጠጥን፡፡ ቢያንስ ለእርሷ ጀርባዬን ሰጥቼ የምቀመጥባቼው ክፍት ወንበሮች ነበሩ፤ ግን ፊት ለፊቷ የምንተያይበት ወንበር ላይ ተጣድኩ፤ ደንብሬ መሆን አለበት፡፡
ድባቡ የሚጨንቅ ነበር፡፡ በመካከላችን እንደ ወተት የነጣ ልብስ የለበሱ ሦስት ከብ ጠረጴዛዎች አሉ። ሁሉም ጠረፔዛዎች ላይ፣ የሚያንጸባርቁ ሹካና ማንኪያዎች ተደርድረው፣ መኸላቼው ላይ፣ ብርጭቆ ውስጥ የቆሙ ደማቅ ጽጌሬዳዎች ተቀምጠዋል። በቀኝ በኩል ባሉት ሰፋፊ ወርደ ሰፊ መስኮቶች ላይ፣ ጣል የተደረጉት ነፋሱ ከውጭ ሲገፋቼው፣ መጋረጃዎቹ የእርጉዝ ሴት ቀሚስ መስለው፣ በአየር ይወጠሩና መልሰው ይረግባሉ፡፡ ነፋስ እያረገዙ ነፋስ የሚያስወርዱ መጋረጃዎች: ለመጀመሪያ ጊዜ ሳገኛት፣ እዚያ አንዱ ነጭ መጋረጃ አጠገብ ያለው ወንበር ላይ ተቀምጣ ነበር ያገኘኋት። በየጥጋጥጉ ከተሰቀሉት ስፒከሮች፣ ለስለስ ያለ ሙዚቃ ይፈሳል፡፡ ከማሂሰላም ኋላ ያለው ግድግዳ፣ በትልቅ “ካንቫስ” ላይ በታተመ ፎቶ ተሸፍኗል፡፡ ስስ ነጫጭ መጋረጃዎች፣ ከውጭ በሚ7ፋቼው ነፋስ ረጋ ብለው ይንቀሳቀሳሉ። የወይን ጠርሙዝ ነው...ዘንበል ብሎ፣ ከውስጡ ወይኑ እንደ ፏፏቴ ቁልቁል ይወርዳል....ቀይ ደም የመሰለ ፏፏቴ...ጨነቀኝ። ቀጥሎ በመጋረጃው በኩል የሚገባው ስስ ነፋስ፣ ወደ አውሎ ነፋስ ተቀይሮ ቤቱን የሚገለባብጠው፣ የጠርሙዙ ወይን ወደ ጎርፍ ተቀይሮ እንደ ባሕር ቤቱን የሚሞላው ...የሆነ እንደዚያ ዓይነት ትርምስ ነገር እንደሚፈጠር ያወቅሁ ያኽል ጨነቀኝ፡፡ ማሂ ሰላም፣ የባሏን እጆች በእጆቿ እያሻሼች በዝምታ ታዬዋለች፤ እሱን ለነካችው፣ የእጇ ልስላሴ እኔን ይሰማኛል፡፡ ባሏ ሳያቋርጥ ያወራል፤ምን እንደሚያወራት እንጃ። ገና በአንድ ዕይታ እንደማታፈቅረው አውቂያለሁ፡፡ዓይኖቼ ሴት ላይ ፈጣን ናቸው። እንኳን አራት ዓመት አብራኝ የቆየች ሴት፣ በታክሲ እየከነፍኩ በቅጽበት የማያት ሴት ፊት ላይ ያለች ተንኮል አልስትም ብል፣ ቢጋነን እንጂ የለዬለት ቅጥፈት አይሆንም፡፡ ማሂሰላምና ባሏ አልተቀላቀሉም ዘይት እና ውሃ ነበሩ፡፡ ስታፈቅር እንደምትሆነው ዓይኖቿ ዙሪያዋን አልረሱም፤ ይቃብዛሉ፤ ዙሪያዋን ትቃኛለች። ስታፈቅር እንደዚያ አይደለችም፡፡ ያፈቀረችው ላይ ብቻ የሚተከሉ ዓይኖች ነበሩ ያሏት። ምስክር ነኝ በእሷ ተፈቅሬ ነበርና፡፡ አንድ ጠባብ ክፍል፣ _ የምታፈቅረው ሰውና ትርኢት የሚያሳይ ዝሆን ተቀምጠው፣ ያንን ዝሆን አየሽው? ብትባል፣
የቱን? የምትል፤ ላፈቀረችው መሰጠት ተፈጥሮዋ የሆነው ማሂሰላም፣ እሱ ላይ ብቻ እልነበሩም ዓይኖቿ።.. አይታኛለች፣ ያውም ገና ስገባ- ከሩቅ፡፡ ከዚያ በኋላ ያለው ድራማ ነበር፡፡ ጥሩ አፍቃሪ እንጂ፤ ጥሩ ተዋናይ አልነበረችም፡፡ ባሏ ጋር በጨረፍታ እያዬኋቼው “ከሩቅ ሲያዩን ይኼን ነበር የምንመስለው?” እላለሁ፣ ለራሴ ...አሁንም ቆንጆ ናት ...አሁንም ቀለል ባለ አለባበስ ነበረች፡፡ከላይ ቀያይ አበባ ጣል ጣል ያለበት፣ ነጭ፣ ሰፊ፣ ስስ ሸሚዝ ለብሳለች ...ጡቶቿ ተለቅ አሉብኝ ...ይኼ ሰውዬ ምን አድርጓቼው ነው!? ...ምናልባት ከአሜሪካ ልኳ ያልሆነ የጡት ማስያዣ አምጥቶላት ይሆናል ማን ያውቃል? መቼስ መተዋወቅ ጊዜ ይፈልጋል፡፡ለማሂ ጡቶች ዓይኔን ጨፍኜ የጡት ማስያዣ ብመርጥ፣ ቁጥሯን አልስተውም፡፡ በዚያ ቅጽበት ያስታወስኩት ነገር፣ በአራት ዓመት ቆይታችን አንድም ስጦታ ሰጥቻት አለማወቄን ነው። በአጋጣሚ ከመደርደሪያው ላይ መጽሐፍ አንስታ ልውሰደው? ካለችኝ ውሰጅው እላታለሁ፤ በቃ። ሸሚዟን ሳይ ድንገት ከስንት ጊዜ በኋላ እቤቴ የረሳችው “የውስጥ ልብስ” ትዝ አለኝ። ከጠረጴዛው ስር እግሯ ይታዬኛል፤ የአንድ እግሯን ጫማ አውልቃ በጫማዋ ትጫዎታለች፤ የቆዬ ልማዷ ነበር። ጸጉሯ ግን ተቀይሯል፣ እንደ በፊቱ በቼልታ አለቀቀችውም፣ በሥርዓት ተሠርቷል። ሲመቼው እንደሚሆነው፣ ጥቁርና የሚያብረቀርቅ ጸጉር፡፡ እንዲህ ጠቁሮ ዓይቼው አላውቅም፤ ዐሥር ጊዜ ጸጉሯን ትነካካለች፡፡ ከሴቶች አጥብቄ የምጠላው ባሕሪ! ሳውቃት እንደዚያ አልነበረችም፡፡ ዓይኖቼ እጅ ሆነው ልስላሴዋ እንዲሰማኝ አድርገውኛል-ሙቀቷም...ሰውነቴ ሲነቃቃ ይሰማኛል፡፡ ፊት ለፊቷ ነው የተቀመጥኩት- ከባሏ ኋላ...መልኩ አይታዬኝም፤ ሁለት ጆሮዎቹ ከርፈፍ ያሉ፣ ከኋላ እንዲሁ ጎልማሳ የሚመስል፣ጸጉሩ ላይ ሽበት ጣል ጣል ያደረገበት፡፡ በትከሻው ላይ አሻግራ ታዬኛለች፣ እንደምታዬኝ ሳላያት አውቃለሁ፡፡ አስተናጋጁ ሊታዘዘኝ መጣ፤ ፊቱ ላይ የእፍረት ፈገግታ አለ፡፡ ያውቀኛል‐ያውቃታል፣ ያውቀናል፡፡ ትንሽ እንደምቆይ ነገርኩት…“ለምን ትቆያለህ? መጥታለች'ኮ!" አለማለቱም ጨዋ ሆኖ ነው፡፡ እስቲ የሚመጣውን ጉድ ልይ! ብሎ ነው መሰል
ትሪውን አቅፎ የታፈነች ዓይንአፋር ፈገግታው ስትከስም አንድ ጥግ ቆመ (እንዲህ ትርኢት ለማዬት ከጓጓ፣ለምን ረዘም ረዘም ያሉ ቢላዋዎች ከወጥቤት አምጥቶ! አንድ ለእኔ፣ አንድ ለባሏ ሰጥቶ ፍልሚያ ጀምሩ አይለንም?) አስተናጋጁ እኔጋ ደርሶ ሲመለስ፣ ድንገት ማሂሰላም ጋር ዓይንለዓይን ተገጣጠምን፡፡ ፊቷ ብስጭትና ጉጉት ሲያንዣብብበት ታዘብኩ። የተበሳጨችበትን ለመረዳት ትንሽ ደቂቃዎች ነበር የወሰደብኝ። እሷ ጋር እዚህ ቤት ስንመጣ ቀድሚያት ከደረስኩ፣ ምንም ነገር ሳላ'ዝ እንደምጠብቃት ታውቃለች፡፡ ምንም አለማዘዝ የሆነች ሴት የመጠበቅ ምልክቴ ነው። ምክንያት ኖሮኝ ሳይሆን፣ ደመነፍሳዊ ልምድ። ጨራርሰው ስለነበር፣ ባሏ የወንበር መደገፊያው ላይ ያንጠለጠለውን ጃኬት ሊያነሳ ዞር ሲል፣ የሆነ ነገር አለቸውና መልሶ ተቀመጠ፡፡ አስተናጋጁን በምልክት ጠርታ ቡና አዘዘች፤ ከሩቅ በከንፈሯ እንቅስቃሴ ነው ቡና ማዘዟን ያወቅኩት
✍ አሌክስ አብርሃም
ክፍል ስድስት
እስከ አሁን እዚህ ነሽ!?
ከተለያዬን ከዓመት በኋላ (በትክክል ዓመት የሞላው እንኳን አይመስለኝም)፣ አዘውትረን እንሄድበት ወደነበረው የሜክሲኮው ሬስቶራንት ሄድኩ። ለነገሩ ከዚያም በፊት ብዙ ጊዜ ሄጃለሁ፡፡ ብቻዬንም፣ ጓደኞቼም ጋር። ትዝታዬ ደብዝዞ ሌላ ትዝታ ቢጻፍበትም፣ እዚያ ቤት በሄድኩ ቁጥር ግን አስታውሳት ነበር። በተለይ እነዚያን ሳያቋርጡ ዘፈን የሚያንቆረቁሩ “ስፒከሮች” ሳይ፣ ማሂሰላምን አስታውሳት ነበር፡፡ ሳልወድ በግድ የዘፈኖቹን ግጥሞች ለማድመጥ እሞክራለሁ "ሰው ሲደሰት ዜማውን፣ ሲያዝን ግጥሙን ይሰማል" ያለው ማን ነበር!?.... የዘፈኖቹን ግጥሞች ለመያዝ አእምሮዬ ይሰንፋል፤ ያውም እኔ...ግጥም እስትንፋሴ ነው የምል እኔ። የዚያን ቀን ቤቱን ስለምወደው፣ እዚያው ሰው ቀጥሬ ነበር... ሴት ቀጥሬ። በዕድሜና በቁመት የምትበልጠኝን ሴት ቀጥሬ፡ አፏ ሥር ተለግቼ፣ ሳቋንና ወሬዋን ሰምቼ የማልጠግብላት ሴት ቀጥሬ፡፡ ስገባ ማንን አገኜሁ?...ማሂሰላምን _ ከእነባሏ...ደነገጥኩ! የእውነት ደነገጥኩ። መጀመሪያ አራት ዓመት አብራኝ የቆዬች ፍቅረኛዬን (አብሮኝ የቆዬ ጠይም ሰውነት ብል ይቀላል) የሆነ ሌላ ሰው ጋር ማዬት በራሱ ለመልመድ ጊዜ የሚወስድ የመደናገር ማዕበል ያስነሳል፡፡ ቀጥሎ ሰላም ማለት አለብኝ ወይስ የለብኝም? የሚል ጥያቄ ይከተላል....ግራ ተጋባሁ፡፡ ትንሽ ምቾት ነሳኝ- ነገሩ ...አልተነጋገርንም ሰላም አልተባባልንም፡፡ ለምን ሰላም እንዳላለችኝ ገርሞኛል፡፡ እንዲያውም እንደማታውቀኝ ዓይኗን እኔ ላይ ላለማሳረፍ ስትጥር ነበር፡፡ ይኼን ነገሯን ሳይ፣ እኔም ሰላም የማለት ዕቅዴን ተውኩትና ሩቅና ሩቅ ሆነን ተፋጠጥን፡፡ ቢያንስ ለእርሷ ጀርባዬን ሰጥቼ የምቀመጥባቼው ክፍት ወንበሮች ነበሩ፤ ግን ፊት ለፊቷ የምንተያይበት ወንበር ላይ ተጣድኩ፤ ደንብሬ መሆን አለበት፡፡
ድባቡ የሚጨንቅ ነበር፡፡ በመካከላችን እንደ ወተት የነጣ ልብስ የለበሱ ሦስት ከብ ጠረጴዛዎች አሉ። ሁሉም ጠረፔዛዎች ላይ፣ የሚያንጸባርቁ ሹካና ማንኪያዎች ተደርድረው፣ መኸላቼው ላይ፣ ብርጭቆ ውስጥ የቆሙ ደማቅ ጽጌሬዳዎች ተቀምጠዋል። በቀኝ በኩል ባሉት ሰፋፊ ወርደ ሰፊ መስኮቶች ላይ፣ ጣል የተደረጉት ነፋሱ ከውጭ ሲገፋቼው፣ መጋረጃዎቹ የእርጉዝ ሴት ቀሚስ መስለው፣ በአየር ይወጠሩና መልሰው ይረግባሉ፡፡ ነፋስ እያረገዙ ነፋስ የሚያስወርዱ መጋረጃዎች: ለመጀመሪያ ጊዜ ሳገኛት፣ እዚያ አንዱ ነጭ መጋረጃ አጠገብ ያለው ወንበር ላይ ተቀምጣ ነበር ያገኘኋት። በየጥጋጥጉ ከተሰቀሉት ስፒከሮች፣ ለስለስ ያለ ሙዚቃ ይፈሳል፡፡ ከማሂሰላም ኋላ ያለው ግድግዳ፣ በትልቅ “ካንቫስ” ላይ በታተመ ፎቶ ተሸፍኗል፡፡ ስስ ነጫጭ መጋረጃዎች፣ ከውጭ በሚ7ፋቼው ነፋስ ረጋ ብለው ይንቀሳቀሳሉ። የወይን ጠርሙዝ ነው...ዘንበል ብሎ፣ ከውስጡ ወይኑ እንደ ፏፏቴ ቁልቁል ይወርዳል....ቀይ ደም የመሰለ ፏፏቴ...ጨነቀኝ። ቀጥሎ በመጋረጃው በኩል የሚገባው ስስ ነፋስ፣ ወደ አውሎ ነፋስ ተቀይሮ ቤቱን የሚገለባብጠው፣ የጠርሙዙ ወይን ወደ ጎርፍ ተቀይሮ እንደ ባሕር ቤቱን የሚሞላው ...የሆነ እንደዚያ ዓይነት ትርምስ ነገር እንደሚፈጠር ያወቅሁ ያኽል ጨነቀኝ፡፡ ማሂ ሰላም፣ የባሏን እጆች በእጆቿ እያሻሼች በዝምታ ታዬዋለች፤ እሱን ለነካችው፣ የእጇ ልስላሴ እኔን ይሰማኛል፡፡ ባሏ ሳያቋርጥ ያወራል፤ምን እንደሚያወራት እንጃ። ገና በአንድ ዕይታ እንደማታፈቅረው አውቂያለሁ፡፡ዓይኖቼ ሴት ላይ ፈጣን ናቸው። እንኳን አራት ዓመት አብራኝ የቆየች ሴት፣ በታክሲ እየከነፍኩ በቅጽበት የማያት ሴት ፊት ላይ ያለች ተንኮል አልስትም ብል፣ ቢጋነን እንጂ የለዬለት ቅጥፈት አይሆንም፡፡ ማሂሰላምና ባሏ አልተቀላቀሉም ዘይት እና ውሃ ነበሩ፡፡ ስታፈቅር እንደምትሆነው ዓይኖቿ ዙሪያዋን አልረሱም፤ ይቃብዛሉ፤ ዙሪያዋን ትቃኛለች። ስታፈቅር እንደዚያ አይደለችም፡፡ ያፈቀረችው ላይ ብቻ የሚተከሉ ዓይኖች ነበሩ ያሏት። ምስክር ነኝ በእሷ ተፈቅሬ ነበርና፡፡ አንድ ጠባብ ክፍል፣ _ የምታፈቅረው ሰውና ትርኢት የሚያሳይ ዝሆን ተቀምጠው፣ ያንን ዝሆን አየሽው? ብትባል፣
የቱን? የምትል፤ ላፈቀረችው መሰጠት ተፈጥሮዋ የሆነው ማሂሰላም፣ እሱ ላይ ብቻ እልነበሩም ዓይኖቿ።.. አይታኛለች፣ ያውም ገና ስገባ- ከሩቅ፡፡ ከዚያ በኋላ ያለው ድራማ ነበር፡፡ ጥሩ አፍቃሪ እንጂ፤ ጥሩ ተዋናይ አልነበረችም፡፡ ባሏ ጋር በጨረፍታ እያዬኋቼው “ከሩቅ ሲያዩን ይኼን ነበር የምንመስለው?” እላለሁ፣ ለራሴ ...አሁንም ቆንጆ ናት ...አሁንም ቀለል ባለ አለባበስ ነበረች፡፡ከላይ ቀያይ አበባ ጣል ጣል ያለበት፣ ነጭ፣ ሰፊ፣ ስስ ሸሚዝ ለብሳለች ...ጡቶቿ ተለቅ አሉብኝ ...ይኼ ሰውዬ ምን አድርጓቼው ነው!? ...ምናልባት ከአሜሪካ ልኳ ያልሆነ የጡት ማስያዣ አምጥቶላት ይሆናል ማን ያውቃል? መቼስ መተዋወቅ ጊዜ ይፈልጋል፡፡ለማሂ ጡቶች ዓይኔን ጨፍኜ የጡት ማስያዣ ብመርጥ፣ ቁጥሯን አልስተውም፡፡ በዚያ ቅጽበት ያስታወስኩት ነገር፣ በአራት ዓመት ቆይታችን አንድም ስጦታ ሰጥቻት አለማወቄን ነው። በአጋጣሚ ከመደርደሪያው ላይ መጽሐፍ አንስታ ልውሰደው? ካለችኝ ውሰጅው እላታለሁ፤ በቃ። ሸሚዟን ሳይ ድንገት ከስንት ጊዜ በኋላ እቤቴ የረሳችው “የውስጥ ልብስ” ትዝ አለኝ። ከጠረጴዛው ስር እግሯ ይታዬኛል፤ የአንድ እግሯን ጫማ አውልቃ በጫማዋ ትጫዎታለች፤ የቆዬ ልማዷ ነበር። ጸጉሯ ግን ተቀይሯል፣ እንደ በፊቱ በቼልታ አለቀቀችውም፣ በሥርዓት ተሠርቷል። ሲመቼው እንደሚሆነው፣ ጥቁርና የሚያብረቀርቅ ጸጉር፡፡ እንዲህ ጠቁሮ ዓይቼው አላውቅም፤ ዐሥር ጊዜ ጸጉሯን ትነካካለች፡፡ ከሴቶች አጥብቄ የምጠላው ባሕሪ! ሳውቃት እንደዚያ አልነበረችም፡፡ ዓይኖቼ እጅ ሆነው ልስላሴዋ እንዲሰማኝ አድርገውኛል-ሙቀቷም...ሰውነቴ ሲነቃቃ ይሰማኛል፡፡ ፊት ለፊቷ ነው የተቀመጥኩት- ከባሏ ኋላ...መልኩ አይታዬኝም፤ ሁለት ጆሮዎቹ ከርፈፍ ያሉ፣ ከኋላ እንዲሁ ጎልማሳ የሚመስል፣ጸጉሩ ላይ ሽበት ጣል ጣል ያደረገበት፡፡ በትከሻው ላይ አሻግራ ታዬኛለች፣ እንደምታዬኝ ሳላያት አውቃለሁ፡፡ አስተናጋጁ ሊታዘዘኝ መጣ፤ ፊቱ ላይ የእፍረት ፈገግታ አለ፡፡ ያውቀኛል‐ያውቃታል፣ ያውቀናል፡፡ ትንሽ እንደምቆይ ነገርኩት…“ለምን ትቆያለህ? መጥታለች'ኮ!" አለማለቱም ጨዋ ሆኖ ነው፡፡ እስቲ የሚመጣውን ጉድ ልይ! ብሎ ነው መሰል
ትሪውን አቅፎ የታፈነች ዓይንአፋር ፈገግታው ስትከስም አንድ ጥግ ቆመ (እንዲህ ትርኢት ለማዬት ከጓጓ፣ለምን ረዘም ረዘም ያሉ ቢላዋዎች ከወጥቤት አምጥቶ! አንድ ለእኔ፣ አንድ ለባሏ ሰጥቶ ፍልሚያ ጀምሩ አይለንም?) አስተናጋጁ እኔጋ ደርሶ ሲመለስ፣ ድንገት ማሂሰላም ጋር ዓይንለዓይን ተገጣጠምን፡፡ ፊቷ ብስጭትና ጉጉት ሲያንዣብብበት ታዘብኩ። የተበሳጨችበትን ለመረዳት ትንሽ ደቂቃዎች ነበር የወሰደብኝ። እሷ ጋር እዚህ ቤት ስንመጣ ቀድሚያት ከደረስኩ፣ ምንም ነገር ሳላ'ዝ እንደምጠብቃት ታውቃለች፡፡ ምንም አለማዘዝ የሆነች ሴት የመጠበቅ ምልክቴ ነው። ምክንያት ኖሮኝ ሳይሆን፣ ደመነፍሳዊ ልምድ። ጨራርሰው ስለነበር፣ ባሏ የወንበር መደገፊያው ላይ ያንጠለጠለውን ጃኬት ሊያነሳ ዞር ሲል፣ የሆነ ነገር አለቸውና መልሶ ተቀመጠ፡፡ አስተናጋጁን በምልክት ጠርታ ቡና አዘዘች፤ ከሩቅ በከንፈሯ እንቅስቃሴ ነው ቡና ማዘዟን ያወቅኩት
👍56🤔2🥰1
"ቡና" ስትል ውብ ከንፈሯ እንደሚያፏጭ ሰው ሰብሰብ ብሎ በትንሹ ከፈት አለ፤ ማሂ ሰላም ቡና አትወድም፣ ለመቆዬትና የቀጠርኳትን ሴት ለማዬት እንደፈለገች ገብቶኛል፡፡ ስልኬን አወጣሁና የቀጠርኳትን ልጅ ይቅርታ ጠይቄ የቀጠሮውን ቦታ ቀዬርኩ፡፡ ተነስቼ ስወጣ ማሂ ያዘዘችውን ቡና ይዞ የሚመጣው ሌላ አስተናጋጅ ጋር ተላለፍን፡፡ እዚህ ቡና ውስጥ ገብቼ ብሟሟ... የሚል ሐሳብ ውልብ አለብኝ፡፡ ላለፈው ሕይወት ቀንቻለሁ፤ ለሚመጣው ደግሞ ጓጉቻለሁ! ሁሉም አይለፈኝ የሚል በሽታ፡፡ በቀጣዩ ቀን ጧት ገና ከእንቅልፌ ሳልነቃ ስልኬ ጠራ...ማሂ ሰላም ነበረች፡፡ ክፉኛ ደንግጫለሁ፡፡ በስንት ጊዜዋ! ልክ ስልኩን ሳነሳው አብረን እንዳደርን ሁሉ ሰላምታ ሳታስቀድም
“ማናት? አብርሽ!'' አለችኝ፡፡ ድምጿ ውስጥ ፍርኃት ነበር፣ ... ቅናት ነበር፣... እልኅ ነበር !
“ሰላምታ አይቀድምም...?" አልኩ የሆነ የአሸናፊነት ስሜት ተሰምቶኛል፣ እስቲ ማሸነፍን ምን አመጣው? “ሰላም!..... አውቃለሁ በአንተ ሕይወት አይመለከተኝም...ግን ማ'ናት?'' የደከማት መሰለች አሁን ደግሞ። “ባክሽ! እሱን ተይው ትላንት አዬሁሽ...በጣም አምሮብሻል። በጣም ነው ያማርሽው፡፡ ለምንድን ነው ሰላም ያላልሽኝ ግን?'' አልኳት፡፡ ልክ ያልኩትን እንዳልሰማች ድርቅ ባለ ድምፅ “ማናት?'' አለችኝ! "ጓደኛዬ ነው!'' በረዢሙ ተነፈሰችና፣ ለራሷ በሚመስል ድምፅ ... “አውቃለሁ! የቀጠርከው ወንድ አልነበረም፣ ውሸት አያምርብህም!'' አለችኝ ፡፡ ዝም ተባብለን ቆዬን፡፡ ከኋላዋ ሙዚቃ ይሰማኛል፡፡ “ለምንድን ነው ግን የማታገባው? ...ቢያንስ በዬሬስቶራንቱ ከመዞር ታርፋለህ" አለችኝ። እንዲሁ ዝም ከማለት የተናገረችው ነገር ነበር የሚመስለው። “አንቺ መቼ አረፍሽ?'' ሳቀች...የሆነ ለስላሳ ድምፅ የሌለው ሳቅ፣ ትንፋሿ ነበር እንደሳቀች የሚያሳብቀው፡፡ ከመጀመሪያው በረዘመ ዝምታ ከቆዬን በኋላ “ስትናፍቀኝ እሄዳለሁ! የእውነት ትናፍቀኛለህ...ምናባቴ ይሻለኛል? ግን'ኮ ጥሩ ሰው አይደለህም፣ ምንሀም ለሴት ጥሩ አይደለም፣ ግን...ትናፍቀኛለህ` ዝም አልኩ...ዝም ተባብለን ቆዬን!...ከኋላዋ ዘፈን ይሰማኛል፡፡ ከረዢም ዝምታ በኋላ ....ለመስማት በሚያስቼግር ድምፅ፣ “አርግዣለሁ" አለችኝ፡፡
ይኽ ከሆነ ከሦስት ዓመት በኋላ ይመስለኛል፣ እዚህ ቦሌ ኤድናሞል የሚባል ሕንፃ ላይ ማሂሰላምን ዳግመኛ አዬኋት፤ አንዲት የምታምር ሕፃን ይዛ። ዓይኔን ማመን አልቻልኩም። ያቺ በአዋቂ ቀራፂ የተሠራች የምትመስል ውብ ሴት የለችም፤ የጤና ነው ወይ? እስከምል በማይታመን ውፍረት ተውጣ ነበር! “ወላድ በድባብ ትሂድ ቆንጆ ሞልቷል” ቢባልም የማይደገሙ መልኮች አሉ፤ የሴት ልጅ ውበት እንደ እጅ አሻራ ነው፤ የአንዷ ሴት ውበት ሌላዋ ላይ ፈጽሞ አይደገምም፤በተለይ የማሂሰላም የሚደገም አይመስለኝም። የኔ ዘመን ማስታወሻዎች፣ የፊታውራሪ ማንትስ ቤትና የከተማዬ ተራራ ብቻ አይደሉም፤ እነዚያ ውብ ሴቶች ናቸው፡፡ ቤት ሲያፈርሱ ቢያንስ ሰበብ አለው “የተሻለ መገንባት ምናምን' የሴት ልጅ ውበት ግን መቼም በምንም የማይተካ ቅርስ ነው። እንደ አበባ የሚከስሙ፣ ቅርጽና ውበታቼው እንዲህ የሚቀዬር ቅርሶች፤ ከትዳር አድማስ ማዶ የሚጠልቁ ውብ የጧት ፀሐዮች፤ ትዳር ስጠላ! እሷን ባላፈቅራትም __ ከአምልኮ የማይተናነስ ጥሞና ውስጥ የሚያስገባኝ ውብ ሰውነቷ፣ በጊዜ እንዳይለወጥ በምን ዓይነት ጥበብ ጠብቄ ባኖርኩት? እል ነበር! ... አሁን በዚያ የለም፤ ፎቶዋ የለኝም፡፡ ፎቶ ሙቀት የለውም ይቀዘቅዛል፣ የቆንጆ ሴት ፎቶ ለእኔ ውበቷን ዘላለማዊ ለማድረግ አድርቀው የሆነ የመስተዋት ቤት ውስጥ እንዳስቀመጧት ውብ ቢራቢሮ ነው፡፡ ነበር ውስጥ ሙቀት የለም!! እንዳገባት በአንደበቷ ሳይሆን በድርጊት፣ በዓይኖቿ በመላ ሰውነቷ ተማጽናኛለች። እያንዳንዱ ቆዳዋ ላይ ያለው ጥቃቅን ሽንቁር፣ ሚሊዮን አፍ ሆኖ በሚሊዮን ቋንቋ ለምኖኛል ... ማንም ቢሆን ለእብደቱ ለደስታው ቋሚ ርስት ይፈልጋል፤ ርስቷን ነው
የነጠቅኋት ... እናም ወደማታውቀው ርስት ተሰደደች የእሷ ወዳልሆነ፤ ባሏ የስደት ምድር እንጂ ሰው አልነበረም። ስደተኛ ገላዋ ስደተኛ ባል አገባ፤ ጠመንጃ አንስታ ሰውነትሀ ርስቴ ነው መልስ አትል ነገር፤ ለጦርነትም እኮ _ጸንቶ የሚቆም ተፋላሚ ያስፈልጋል፡፡ የሐሴት ምርት ያፈስኩበት ችግኝ ሆኜ መጥቼ ዛፍ የሆንኩበት፣ እንቡጥ ሆኜ መጥቼ አበባ የሆንኩበት፣ ንብ ነህ ወዳጄ ስታርፍብኝ “ኔክታሬን' ስትቀስም አልከለከልኩህም፤ አሳልፈህ ዝንብ እንዲሰፍርብኝ ለምን ተውከኝ!?... የሚል ሙሾ ይወርዳል በሐሳቤ፡፡ ከጀርባዋ ዝም ብዬ አዬኋት ከምንም በላይ የገረመኝ ማሂ ሰላም ተረከዘ ረዥም ጫማ ተጫምታ ነበር። ጠይምነቷ ወደ ቀይ ዳማነት መንገድ ጀምሯል (ወይስ ሜካፕ ተጠቅማ ይሆን?) ዝም ብዬ አዬኋት፤ የመኪና ቁልፍ አንጠልጥላለች- ከንቱ! ውድ ቦርሳ ይዛለች- ከንቱ! ውድ ስልክ ይዛለች- ከንቱ! አለባበሷ የሐብታም ሴት ወይዘሮ ይመስላል- ከንቱ! ያቺ ለአካባቢዋ ግድ የለሽ የነበረች ልጅ አንዴ ልብሷን አንዴ ጸጉሯን ታስተካክላለች፣ አካባቢዋን ቀና እያለች ትቃኛለች፣ እንደ ጅራታም ኮከብ ትጣደፋለች፤ እኔ ውስጥ ግን ልክ እንደ ማታ ጀምበር በቀስታ ነበር የጠለቀችው፡፡ ከጎኗ ድክ ድክ የምትል ልጇ ጋር ...ሄደች ...ሄደች ... ሄደች ...ሄደች... ።
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
“ማናት? አብርሽ!'' አለችኝ፡፡ ድምጿ ውስጥ ፍርኃት ነበር፣ ... ቅናት ነበር፣... እልኅ ነበር !
“ሰላምታ አይቀድምም...?" አልኩ የሆነ የአሸናፊነት ስሜት ተሰምቶኛል፣ እስቲ ማሸነፍን ምን አመጣው? “ሰላም!..... አውቃለሁ በአንተ ሕይወት አይመለከተኝም...ግን ማ'ናት?'' የደከማት መሰለች አሁን ደግሞ። “ባክሽ! እሱን ተይው ትላንት አዬሁሽ...በጣም አምሮብሻል። በጣም ነው ያማርሽው፡፡ ለምንድን ነው ሰላም ያላልሽኝ ግን?'' አልኳት፡፡ ልክ ያልኩትን እንዳልሰማች ድርቅ ባለ ድምፅ “ማናት?'' አለችኝ! "ጓደኛዬ ነው!'' በረዢሙ ተነፈሰችና፣ ለራሷ በሚመስል ድምፅ ... “አውቃለሁ! የቀጠርከው ወንድ አልነበረም፣ ውሸት አያምርብህም!'' አለችኝ ፡፡ ዝም ተባብለን ቆዬን፡፡ ከኋላዋ ሙዚቃ ይሰማኛል፡፡ “ለምንድን ነው ግን የማታገባው? ...ቢያንስ በዬሬስቶራንቱ ከመዞር ታርፋለህ" አለችኝ። እንዲሁ ዝም ከማለት የተናገረችው ነገር ነበር የሚመስለው። “አንቺ መቼ አረፍሽ?'' ሳቀች...የሆነ ለስላሳ ድምፅ የሌለው ሳቅ፣ ትንፋሿ ነበር እንደሳቀች የሚያሳብቀው፡፡ ከመጀመሪያው በረዘመ ዝምታ ከቆዬን በኋላ “ስትናፍቀኝ እሄዳለሁ! የእውነት ትናፍቀኛለህ...ምናባቴ ይሻለኛል? ግን'ኮ ጥሩ ሰው አይደለህም፣ ምንሀም ለሴት ጥሩ አይደለም፣ ግን...ትናፍቀኛለህ` ዝም አልኩ...ዝም ተባብለን ቆዬን!...ከኋላዋ ዘፈን ይሰማኛል፡፡ ከረዢም ዝምታ በኋላ ....ለመስማት በሚያስቼግር ድምፅ፣ “አርግዣለሁ" አለችኝ፡፡
ይኽ ከሆነ ከሦስት ዓመት በኋላ ይመስለኛል፣ እዚህ ቦሌ ኤድናሞል የሚባል ሕንፃ ላይ ማሂሰላምን ዳግመኛ አዬኋት፤ አንዲት የምታምር ሕፃን ይዛ። ዓይኔን ማመን አልቻልኩም። ያቺ በአዋቂ ቀራፂ የተሠራች የምትመስል ውብ ሴት የለችም፤ የጤና ነው ወይ? እስከምል በማይታመን ውፍረት ተውጣ ነበር! “ወላድ በድባብ ትሂድ ቆንጆ ሞልቷል” ቢባልም የማይደገሙ መልኮች አሉ፤ የሴት ልጅ ውበት እንደ እጅ አሻራ ነው፤ የአንዷ ሴት ውበት ሌላዋ ላይ ፈጽሞ አይደገምም፤በተለይ የማሂሰላም የሚደገም አይመስለኝም። የኔ ዘመን ማስታወሻዎች፣ የፊታውራሪ ማንትስ ቤትና የከተማዬ ተራራ ብቻ አይደሉም፤ እነዚያ ውብ ሴቶች ናቸው፡፡ ቤት ሲያፈርሱ ቢያንስ ሰበብ አለው “የተሻለ መገንባት ምናምን' የሴት ልጅ ውበት ግን መቼም በምንም የማይተካ ቅርስ ነው። እንደ አበባ የሚከስሙ፣ ቅርጽና ውበታቼው እንዲህ የሚቀዬር ቅርሶች፤ ከትዳር አድማስ ማዶ የሚጠልቁ ውብ የጧት ፀሐዮች፤ ትዳር ስጠላ! እሷን ባላፈቅራትም __ ከአምልኮ የማይተናነስ ጥሞና ውስጥ የሚያስገባኝ ውብ ሰውነቷ፣ በጊዜ እንዳይለወጥ በምን ዓይነት ጥበብ ጠብቄ ባኖርኩት? እል ነበር! ... አሁን በዚያ የለም፤ ፎቶዋ የለኝም፡፡ ፎቶ ሙቀት የለውም ይቀዘቅዛል፣ የቆንጆ ሴት ፎቶ ለእኔ ውበቷን ዘላለማዊ ለማድረግ አድርቀው የሆነ የመስተዋት ቤት ውስጥ እንዳስቀመጧት ውብ ቢራቢሮ ነው፡፡ ነበር ውስጥ ሙቀት የለም!! እንዳገባት በአንደበቷ ሳይሆን በድርጊት፣ በዓይኖቿ በመላ ሰውነቷ ተማጽናኛለች። እያንዳንዱ ቆዳዋ ላይ ያለው ጥቃቅን ሽንቁር፣ ሚሊዮን አፍ ሆኖ በሚሊዮን ቋንቋ ለምኖኛል ... ማንም ቢሆን ለእብደቱ ለደስታው ቋሚ ርስት ይፈልጋል፤ ርስቷን ነው
የነጠቅኋት ... እናም ወደማታውቀው ርስት ተሰደደች የእሷ ወዳልሆነ፤ ባሏ የስደት ምድር እንጂ ሰው አልነበረም። ስደተኛ ገላዋ ስደተኛ ባል አገባ፤ ጠመንጃ አንስታ ሰውነትሀ ርስቴ ነው መልስ አትል ነገር፤ ለጦርነትም እኮ _ጸንቶ የሚቆም ተፋላሚ ያስፈልጋል፡፡ የሐሴት ምርት ያፈስኩበት ችግኝ ሆኜ መጥቼ ዛፍ የሆንኩበት፣ እንቡጥ ሆኜ መጥቼ አበባ የሆንኩበት፣ ንብ ነህ ወዳጄ ስታርፍብኝ “ኔክታሬን' ስትቀስም አልከለከልኩህም፤ አሳልፈህ ዝንብ እንዲሰፍርብኝ ለምን ተውከኝ!?... የሚል ሙሾ ይወርዳል በሐሳቤ፡፡ ከጀርባዋ ዝም ብዬ አዬኋት ከምንም በላይ የገረመኝ ማሂ ሰላም ተረከዘ ረዥም ጫማ ተጫምታ ነበር። ጠይምነቷ ወደ ቀይ ዳማነት መንገድ ጀምሯል (ወይስ ሜካፕ ተጠቅማ ይሆን?) ዝም ብዬ አዬኋት፤ የመኪና ቁልፍ አንጠልጥላለች- ከንቱ! ውድ ቦርሳ ይዛለች- ከንቱ! ውድ ስልክ ይዛለች- ከንቱ! አለባበሷ የሐብታም ሴት ወይዘሮ ይመስላል- ከንቱ! ያቺ ለአካባቢዋ ግድ የለሽ የነበረች ልጅ አንዴ ልብሷን አንዴ ጸጉሯን ታስተካክላለች፣ አካባቢዋን ቀና እያለች ትቃኛለች፣ እንደ ጅራታም ኮከብ ትጣደፋለች፤ እኔ ውስጥ ግን ልክ እንደ ማታ ጀምበር በቀስታ ነበር የጠለቀችው፡፡ ከጎኗ ድክ ድክ የምትል ልጇ ጋር ...ሄደች ...ሄደች ... ሄደች ...ሄደች... ።
ይቀጥላል...
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
👍44❤5😁5😢3
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ዶ/ር ሶፊያ ከአራት ወራት ቆይታ በኃላ ነበር ለሌላ ስራ ወደ ሀዋሳ የተመለሰችው፡፡ዛሬ አምስተኛ ቀኗ ነው፡፡መቼስ የሀዋሳ ውበት
ይበልጥ ፈክቶ ይበልጥ ጎልቶ የሚታየው በገዛ
እግር በዝግታ እየተጓዙ ሲያጣጥሙት ነው፡፡
ዶ/ር ሶፊያም ይሄንን እውነት በመገንዘብ
የእለቱን ስራዋን ካጠናቀቀች በኃላ የምሽቱን
አየር ነፋሻማነትና ተስማሚነትንም ከግምት
በማስገባት በእግር ዞር ዞር ለማለት ወሰነችና መኪናዋን ሆቴል ግቢ ውስጥ ትታ በእግሯ ወጣች፡፡ለ3ዐ ደቂቃ በከተማው ተሸከረከረች፡፡
ጉዞዋ አስደሳችና መንፈሷን ያረጋጋላት ቢሆንም ደከማት፤ ወደ ካፌ ጎራ ብላ እረፍት ለመውሰድ ከወሰነች በኃላ መልሳ ሀሳቧን
ቀየረችና ጫማዋን እያስጠረገች ወጪ
ወራጁን መቃኘት እንደሚሻላት አመነች፡፡
ባለችበት አስፓልት አቅጣጫ ጠርዝ ላይ
ወዳለው ሊስትሮ አመራች፡፡ ሊስትሮው ከጐኑ በግምት መቶ የሚሆኑ መፅሀፎች ለሽያጭ ዘርግቷል፡፡እሱም ሊስትሮ ወንበሩ ላይ ቁጭ ብሎ በተመስጦ እያነበበ ነው፡፡ተጠጋችው ፤ግንብ አጥር ተደግፎ የሚገኘው አግዳሚ ወንበር ላይ ቁጭ አለች፡፡
‹‹አንተ ነህ የምትጠርገው?››
ቀና ሳይል <<አዎ እኔ ነኝ፡፡ግን አሁን ስራ ስለያዝኩ እዛ ማዶ ያለው ልጅ ጋር ብታስጠርጊ››አላት በትህትና፡፡
ደነገጠች<< ...አዋ እራሱ ነው፡፡››አወቀችው ፡፡ የዛሬ ወር ሚኒባስ ውስጥ 2ዐዐ ብር ያበደራት ልጅ፡፡ ደነቃት፡፡ በምንም አይነት ሊስትሮና መፅሀፍ ሻጭ ይሆናል ብላ አልገመተችም
ነበር::
<<ችግር የለም ጨርስና ትጠርግልኛለህ ... አልቸኩልም፡፡››አለችው፡፡
ንባቡን እንደቀጠለ ‹‹እንደተመቸሽ፡፡››አላት ፡፡
ከአስር ደቂቃ ጥበቃ በኃላ የሚያነበውን መፅሀፍ አጥፎ አስቀመጠና ቀናም ብሎ ሳያያት ወደ መሬት ወርዶ እግሯን የሊስትሮ ዕቃው ላይ እስክታስቀምጥ ጠብቆ ጫማዋን ያፀዳላት ጀመር፡፡
‹‹‹ይቅርታ የምንተዋወቅ መሰለኝ?››አለችው፡፡
ቀናም ብሎ ሳያያት ‹‹ይሆናል፡፡››
‹‹አስታወስከኝ ግን?››
‹‹ስለአንቺ እያሰብኩ ስላልነበረ አላስታወስኩሽም፡፡››
‹‹አንድ ቀን ከአዲስአባ ስንመጣ ሚኒባስ ውስጥ ብር አበድረኸኝ ነበር››
ማንነቷን ለማረጋገጥ ቀናም ብሎ ሳያያት ስራው ላይ እንዳቀረቀረ ‹‹አስታወስኩ፡፡››አላት፡፡
‹‹እንዴት እንደዛ ትሸውደኛለህ ግን?››
‹‹መስሎሽ ነው፡፡››
<< መስሎኝማ አይደለም፡፡በወቅቱ አንተን ለማግኘት እኮ ሀዋሳን ቀላል አላሰስኮትም፡፡››
‹‹እኔን ለመፈለግ እኮ የዛን ያህል መልፋት አልነበረብሽም፡፡እኔ ማለት ያ ዕብድ ነኝ፣እኔ ማለት ያቺ ሁለት ልጆች ስሯ አስተኝታ የምትለምነው እናት ትታይሻለች ..እሷ ማለት ነኝ፣እኔ ማለት የተራበ ጨቅላ፣የታረዘ አዛውንት ማለት ነኝ፡፡››
‹‹እሱ ገብቶኛል፡፡ባልከው መንገድም ለማድረግ ሞክሬያለው ግን ደግሞ አንተንም አግኝቼ ማመስገን ውስጤ በጣም ፈለገ፡፡››
‹‹እሺ ይሁን፤ምስጋናውን ተቀብዬለሁ፡፡››
‹‹እንደዚህማ በደረቁ አይሆንም፤ ቢያንስ እራት ጋብዤህ ነው ማመስገን የምፈልገው፡፡››
‹‹ደስ ይለኝ ነበር ፤እኔ ግን እራት የምበላው ከጓደኞቼ ጋር ነው፡፡ >>
‹‹‹ምን ችግር አለው ታዲያ ፤ደውልላቸውና ይምጡ፤አብረን እንበላለን፡፡›› በቀላሉ ልትለቀው አልፈለገችም፡፡
‹‹ስልክ የለኝም፤እነሱም የላቸውም፤ቤት ነው ሚጠብቁኝ፡፡››
<<በቃ ችግር የለውም ፤አብረን እንሄድና ይዘናቸው እንወጣለን፡፡››
‹‹ለምን ትቸገሪያለሽ?››
‹‹አልተቸገርኩም፡፡››
<<እኛ የምንበላው እዛው ሰፈር ነው፤ያ ደግሞ ላንቺ የሚመችሽ ቦታ አይደለም፡፡››
‹‹ግድ የለም ይመቸኛል፡፡››
‹‹እንግዲያው እኔ አንድ ሰዓት ነው ከዚህ የምነሳው፤አሁን 12 ሰዓት ነው ፤ለአንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ አካባቢ ተመልሰሽ ነይ፡፡ >>
‹‹አይ እዚሁ እጠብቅሀለው፡፡››አለችው፡፡
አፍጥጦ አያት፡፡ሰው እንደዚህ ችክ ሲልበት አይወድም፡፡‹‹ ግን ምን ቸገረኝ፤የራሷ ጉዳይ... መቀመጡ ሲደክማት ተነስታ ትሄድ የለ›› ብሎ ወደ ንባቡ ተመለሰ፡፡እሷም ወጪ ወራጁን እያየች ስለ እሱ ማሰብ ጀመረች ፡፡በአጋጣሚ በእጇ ገብቶማ ዳግመኛ አያመልጣትም፡፡ 12፡ 3ዐ ላይ ስልኳ ጮኸ ፡፡ አነሳችው፡፡ የቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱ ስራ አስኪያጅ ነው፡፡
‹‹ሄሎ ልዑል፡፡››
‹‹አመሰግናለሁ..ሌላ ቀጠሮ አለብኝ፡፡››
‹‹አዎ ፡፡አንድ የድሮ የልብ ጓደኛዬን በአጋጣሚ አግኝቼ እራት ካልጋበዝኩሽ ስላለ ከእሱ ጋር ነው የማመሸው፡፡››
‹‹እሺ..ቻው አመሰግናለሁ፡፡››
ለአንድ እሩብ ጉዳይ መፅሀፎቹን ሰበሰበና በቦርሳውን ጠቀጠቃቸው፡፡ አንዱን በአንድ ተከሻው ሌላውን በሌላ ትከሻው አነገተና የሊስትሮ ሳጥኑን በቀኝ እጁ በመያዝ
መንገዱን ቀጠለ፡፡ተከተለችው፡፡እሷ እሱ የገረማትን ያህል እሱም ገርማዋለች፡፡ እንዲህ ችኮ ሴት ገጥሞት አያውቅም፡፡.
ወደ እሱ ቤት ጉዞ ጀምረው ግማሽ መንገድ ላይ እንደደረሱ‹‹ስሜን አልጠየቅከኝም?›› አለችው ፡፡
‹‹ስላላስፈለገኝ ነው ያልጠየቅኩሽ›› አላት፡፡
‹‹መተዋወቅ እኮ ክፋት የለውም፡፡››
‹‹ክፋት አለው መች ወጣኝ?፡፡››
‹‹ሶፊያ እባላለሁ...ያንተስ?››
‹‹ከዚህ በፊት በፈለገሽው ስም ልትጠሪኝ ትችያለሽ ብዬሽ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ስም መለያ ነው፣እኔነቴን አይወክልም፡፡ አንቺ እኔን ከሌላ የሰው ልጅ ለይተሸ ለመጥራት ያስፈልገኛል ካልሽ የሚመችሽን ተጠቀሚ፡፡››
‹‹ሶቅራጦስ ይመችሀል?››
‹‹ዋናው ላንቺ ይመችሽ፡፡ይሄን ስም በፊት አንድ ታላቅና ቅዱስ ሰው ተጠቅሞበታል፡፡››
‹‹አውቃለሁ፤እኔም ለዛ ነው የመረጥኩት።
‹‹ደግ›› ይሄንን ሁሉ ሲያወሩ ብዙ የዉስጥ ለውስጥ መንገዶችን አልፈው ነበር፡፡ ግንብ አጥር ያለው ቤት ጋር ሲደርሱ የሊስትሮውን ዕቃ መሬት አስቀመጠና ከኪሱ በማውጣት መክፈት ጀመረ፡፡
‹‹5 ደቂቃ ጠብቂኝ መጣሁ፡፡ ››ብሏት እንደተገተረች ጥሏት ወደ ውስጥ ገባ ብትፈራም ጭለማ ውስጥ ቆማ መጠበቅ ጀመረች፡፡ ሰዓቱ አንድ ሰዓት ከሩብ ሆኗል በአራት ህፃናት ተከቦ መጣ፡፡ ሁሉም እየቧረቁ ስሩ ኩስ ኩስ ይላሉ፡፡የሁሉዎ ተቀራራቢ ነው በ7 እና በ12 ዓመት መሀል ሲሆን ከአራቱ ሦስቱ ሴቶች ናቸው
‹‹ጓደኞችህስ?››
‹‹እኚው›› አላት ወደ ልጆቹ እየጠቆመ፡፡
ከፈለግሽ ተከተይን በማለት ከእነሱ ጋር በፈገግታ እያወራና እየተሳሳቀ ቀድሟት መንገዱን ቀጠለ፡፡ ብዙም ከማይርቅ አንድ መንገድ ዳር ካለ ደከም ያለ ምግብ ቤት ገቡ ፡፡ ተከትለቻቸው፡፡አንድ ጠረጴዛ ከበው ተቀመጡ፡፡አንድ ለእሷም ሳበላት ፤ ተቀመጠች፡፡
እርጅና የተጫጫናቸው አሮጊት ከጓዲያ ወጡና‹‹ ... ልጆቼ መጣችሁ? በስንት ጊዜያችሁ ፤ናፍቃችሁኝ ነበር፡፡››
‹‹ሰላም ኖት ማዘር?››ታዲዬስ ነው፡፡
‹‹ሰላም ነኝ ፤ይመስገነው፡፡ደግሞ እንግዳ ይዛችሁ ነው የመጣችሁት?››
‹‹አዎ... ምግብ ቤት አጥታ ስትንከራተት መንገድ ላይ አግኝተናት ነው ይዘናት የመጣነው፡፡››
‹‹በሞትኩት.. ለሀገሩ እንግዳ ነቻ?››መጣሁ ብለው ተመልሰው ወደ ውስጥ ገቡ፡፡
‹‹ስምሽ ማን ነው? አለቻት ጎኗ የተቀመጠችውን ትንሽ ልጅ ፡፡
‹‹ሶፊያ..ያንቺስ?››
<<ሚጣ ነው?»
‹‹ሚጣ ታዲዬስ››
‹‹እሱ ምንሽ ነው? አለቻት በጣቷ እየጠቆመች፡፡እሱን ቀጥታ ጠይቃ ማይሆን መልስ ሰጥቷት ከምትበሳጭ በጎን ትክክለኛ ስሙን ለማወቅ መሞከሯ ነበር፡፡
በተኮላተፈ አንደበት‹‹አባቴ›› ብላ መለሰችላት
‹‹አንቺስ እናት ስምሽ ማነው?››
<<ሄለን>>
<<ሄለን ማ?>>
‹‹ሄለን ታዲወስ››
‹‹አባትሽ ታዲወስ የታለ?››
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ዶ/ር ሶፊያ ከአራት ወራት ቆይታ በኃላ ነበር ለሌላ ስራ ወደ ሀዋሳ የተመለሰችው፡፡ዛሬ አምስተኛ ቀኗ ነው፡፡መቼስ የሀዋሳ ውበት
ይበልጥ ፈክቶ ይበልጥ ጎልቶ የሚታየው በገዛ
እግር በዝግታ እየተጓዙ ሲያጣጥሙት ነው፡፡
ዶ/ር ሶፊያም ይሄንን እውነት በመገንዘብ
የእለቱን ስራዋን ካጠናቀቀች በኃላ የምሽቱን
አየር ነፋሻማነትና ተስማሚነትንም ከግምት
በማስገባት በእግር ዞር ዞር ለማለት ወሰነችና መኪናዋን ሆቴል ግቢ ውስጥ ትታ በእግሯ ወጣች፡፡ለ3ዐ ደቂቃ በከተማው ተሸከረከረች፡፡
ጉዞዋ አስደሳችና መንፈሷን ያረጋጋላት ቢሆንም ደከማት፤ ወደ ካፌ ጎራ ብላ እረፍት ለመውሰድ ከወሰነች በኃላ መልሳ ሀሳቧን
ቀየረችና ጫማዋን እያስጠረገች ወጪ
ወራጁን መቃኘት እንደሚሻላት አመነች፡፡
ባለችበት አስፓልት አቅጣጫ ጠርዝ ላይ
ወዳለው ሊስትሮ አመራች፡፡ ሊስትሮው ከጐኑ በግምት መቶ የሚሆኑ መፅሀፎች ለሽያጭ ዘርግቷል፡፡እሱም ሊስትሮ ወንበሩ ላይ ቁጭ ብሎ በተመስጦ እያነበበ ነው፡፡ተጠጋችው ፤ግንብ አጥር ተደግፎ የሚገኘው አግዳሚ ወንበር ላይ ቁጭ አለች፡፡
‹‹አንተ ነህ የምትጠርገው?››
ቀና ሳይል <<አዎ እኔ ነኝ፡፡ግን አሁን ስራ ስለያዝኩ እዛ ማዶ ያለው ልጅ ጋር ብታስጠርጊ››አላት በትህትና፡፡
ደነገጠች<< ...አዋ እራሱ ነው፡፡››አወቀችው ፡፡ የዛሬ ወር ሚኒባስ ውስጥ 2ዐዐ ብር ያበደራት ልጅ፡፡ ደነቃት፡፡ በምንም አይነት ሊስትሮና መፅሀፍ ሻጭ ይሆናል ብላ አልገመተችም
ነበር::
<<ችግር የለም ጨርስና ትጠርግልኛለህ ... አልቸኩልም፡፡››አለችው፡፡
ንባቡን እንደቀጠለ ‹‹እንደተመቸሽ፡፡››አላት ፡፡
ከአስር ደቂቃ ጥበቃ በኃላ የሚያነበውን መፅሀፍ አጥፎ አስቀመጠና ቀናም ብሎ ሳያያት ወደ መሬት ወርዶ እግሯን የሊስትሮ ዕቃው ላይ እስክታስቀምጥ ጠብቆ ጫማዋን ያፀዳላት ጀመር፡፡
‹‹‹ይቅርታ የምንተዋወቅ መሰለኝ?››አለችው፡፡
ቀናም ብሎ ሳያያት ‹‹ይሆናል፡፡››
‹‹አስታወስከኝ ግን?››
‹‹ስለአንቺ እያሰብኩ ስላልነበረ አላስታወስኩሽም፡፡››
‹‹አንድ ቀን ከአዲስአባ ስንመጣ ሚኒባስ ውስጥ ብር አበድረኸኝ ነበር››
ማንነቷን ለማረጋገጥ ቀናም ብሎ ሳያያት ስራው ላይ እንዳቀረቀረ ‹‹አስታወስኩ፡፡››አላት፡፡
‹‹እንዴት እንደዛ ትሸውደኛለህ ግን?››
‹‹መስሎሽ ነው፡፡››
<< መስሎኝማ አይደለም፡፡በወቅቱ አንተን ለማግኘት እኮ ሀዋሳን ቀላል አላሰስኮትም፡፡››
‹‹እኔን ለመፈለግ እኮ የዛን ያህል መልፋት አልነበረብሽም፡፡እኔ ማለት ያ ዕብድ ነኝ፣እኔ ማለት ያቺ ሁለት ልጆች ስሯ አስተኝታ የምትለምነው እናት ትታይሻለች ..እሷ ማለት ነኝ፣እኔ ማለት የተራበ ጨቅላ፣የታረዘ አዛውንት ማለት ነኝ፡፡››
‹‹እሱ ገብቶኛል፡፡ባልከው መንገድም ለማድረግ ሞክሬያለው ግን ደግሞ አንተንም አግኝቼ ማመስገን ውስጤ በጣም ፈለገ፡፡››
‹‹እሺ ይሁን፤ምስጋናውን ተቀብዬለሁ፡፡››
‹‹እንደዚህማ በደረቁ አይሆንም፤ ቢያንስ እራት ጋብዤህ ነው ማመስገን የምፈልገው፡፡››
‹‹ደስ ይለኝ ነበር ፤እኔ ግን እራት የምበላው ከጓደኞቼ ጋር ነው፡፡ >>
‹‹‹ምን ችግር አለው ታዲያ ፤ደውልላቸውና ይምጡ፤አብረን እንበላለን፡፡›› በቀላሉ ልትለቀው አልፈለገችም፡፡
‹‹ስልክ የለኝም፤እነሱም የላቸውም፤ቤት ነው ሚጠብቁኝ፡፡››
<<በቃ ችግር የለውም ፤አብረን እንሄድና ይዘናቸው እንወጣለን፡፡››
‹‹ለምን ትቸገሪያለሽ?››
‹‹አልተቸገርኩም፡፡››
<<እኛ የምንበላው እዛው ሰፈር ነው፤ያ ደግሞ ላንቺ የሚመችሽ ቦታ አይደለም፡፡››
‹‹ግድ የለም ይመቸኛል፡፡››
‹‹እንግዲያው እኔ አንድ ሰዓት ነው ከዚህ የምነሳው፤አሁን 12 ሰዓት ነው ፤ለአንድ ሰዓት ሩብ ጉዳይ አካባቢ ተመልሰሽ ነይ፡፡ >>
‹‹አይ እዚሁ እጠብቅሀለው፡፡››አለችው፡፡
አፍጥጦ አያት፡፡ሰው እንደዚህ ችክ ሲልበት አይወድም፡፡‹‹ ግን ምን ቸገረኝ፤የራሷ ጉዳይ... መቀመጡ ሲደክማት ተነስታ ትሄድ የለ›› ብሎ ወደ ንባቡ ተመለሰ፡፡እሷም ወጪ ወራጁን እያየች ስለ እሱ ማሰብ ጀመረች ፡፡በአጋጣሚ በእጇ ገብቶማ ዳግመኛ አያመልጣትም፡፡ 12፡ 3ዐ ላይ ስልኳ ጮኸ ፡፡ አነሳችው፡፡ የቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱ ስራ አስኪያጅ ነው፡፡
‹‹ሄሎ ልዑል፡፡››
‹‹አመሰግናለሁ..ሌላ ቀጠሮ አለብኝ፡፡››
‹‹አዎ ፡፡አንድ የድሮ የልብ ጓደኛዬን በአጋጣሚ አግኝቼ እራት ካልጋበዝኩሽ ስላለ ከእሱ ጋር ነው የማመሸው፡፡››
‹‹እሺ..ቻው አመሰግናለሁ፡፡››
ለአንድ እሩብ ጉዳይ መፅሀፎቹን ሰበሰበና በቦርሳውን ጠቀጠቃቸው፡፡ አንዱን በአንድ ተከሻው ሌላውን በሌላ ትከሻው አነገተና የሊስትሮ ሳጥኑን በቀኝ እጁ በመያዝ
መንገዱን ቀጠለ፡፡ተከተለችው፡፡እሷ እሱ የገረማትን ያህል እሱም ገርማዋለች፡፡ እንዲህ ችኮ ሴት ገጥሞት አያውቅም፡፡.
ወደ እሱ ቤት ጉዞ ጀምረው ግማሽ መንገድ ላይ እንደደረሱ‹‹ስሜን አልጠየቅከኝም?›› አለችው ፡፡
‹‹ስላላስፈለገኝ ነው ያልጠየቅኩሽ›› አላት፡፡
‹‹መተዋወቅ እኮ ክፋት የለውም፡፡››
‹‹ክፋት አለው መች ወጣኝ?፡፡››
‹‹ሶፊያ እባላለሁ...ያንተስ?››
‹‹ከዚህ በፊት በፈለገሽው ስም ልትጠሪኝ ትችያለሽ ብዬሽ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ስም መለያ ነው፣እኔነቴን አይወክልም፡፡ አንቺ እኔን ከሌላ የሰው ልጅ ለይተሸ ለመጥራት ያስፈልገኛል ካልሽ የሚመችሽን ተጠቀሚ፡፡››
‹‹ሶቅራጦስ ይመችሀል?››
‹‹ዋናው ላንቺ ይመችሽ፡፡ይሄን ስም በፊት አንድ ታላቅና ቅዱስ ሰው ተጠቅሞበታል፡፡››
‹‹አውቃለሁ፤እኔም ለዛ ነው የመረጥኩት።
‹‹ደግ›› ይሄንን ሁሉ ሲያወሩ ብዙ የዉስጥ ለውስጥ መንገዶችን አልፈው ነበር፡፡ ግንብ አጥር ያለው ቤት ጋር ሲደርሱ የሊስትሮውን ዕቃ መሬት አስቀመጠና ከኪሱ በማውጣት መክፈት ጀመረ፡፡
‹‹5 ደቂቃ ጠብቂኝ መጣሁ፡፡ ››ብሏት እንደተገተረች ጥሏት ወደ ውስጥ ገባ ብትፈራም ጭለማ ውስጥ ቆማ መጠበቅ ጀመረች፡፡ ሰዓቱ አንድ ሰዓት ከሩብ ሆኗል በአራት ህፃናት ተከቦ መጣ፡፡ ሁሉም እየቧረቁ ስሩ ኩስ ኩስ ይላሉ፡፡የሁሉዎ ተቀራራቢ ነው በ7 እና በ12 ዓመት መሀል ሲሆን ከአራቱ ሦስቱ ሴቶች ናቸው
‹‹ጓደኞችህስ?››
‹‹እኚው›› አላት ወደ ልጆቹ እየጠቆመ፡፡
ከፈለግሽ ተከተይን በማለት ከእነሱ ጋር በፈገግታ እያወራና እየተሳሳቀ ቀድሟት መንገዱን ቀጠለ፡፡ ብዙም ከማይርቅ አንድ መንገድ ዳር ካለ ደከም ያለ ምግብ ቤት ገቡ ፡፡ ተከትለቻቸው፡፡አንድ ጠረጴዛ ከበው ተቀመጡ፡፡አንድ ለእሷም ሳበላት ፤ ተቀመጠች፡፡
እርጅና የተጫጫናቸው አሮጊት ከጓዲያ ወጡና‹‹ ... ልጆቼ መጣችሁ? በስንት ጊዜያችሁ ፤ናፍቃችሁኝ ነበር፡፡››
‹‹ሰላም ኖት ማዘር?››ታዲዬስ ነው፡፡
‹‹ሰላም ነኝ ፤ይመስገነው፡፡ደግሞ እንግዳ ይዛችሁ ነው የመጣችሁት?››
‹‹አዎ... ምግብ ቤት አጥታ ስትንከራተት መንገድ ላይ አግኝተናት ነው ይዘናት የመጣነው፡፡››
‹‹በሞትኩት.. ለሀገሩ እንግዳ ነቻ?››መጣሁ ብለው ተመልሰው ወደ ውስጥ ገቡ፡፡
‹‹ስምሽ ማን ነው? አለቻት ጎኗ የተቀመጠችውን ትንሽ ልጅ ፡፡
‹‹ሶፊያ..ያንቺስ?››
<<ሚጣ ነው?»
‹‹ሚጣ ታዲዬስ››
‹‹እሱ ምንሽ ነው? አለቻት በጣቷ እየጠቆመች፡፡እሱን ቀጥታ ጠይቃ ማይሆን መልስ ሰጥቷት ከምትበሳጭ በጎን ትክክለኛ ስሙን ለማወቅ መሞከሯ ነበር፡፡
በተኮላተፈ አንደበት‹‹አባቴ›› ብላ መለሰችላት
‹‹አንቺስ እናት ስምሽ ማነው?››
<<ሄለን>>
<<ሄለን ማ?>>
‹‹ሄለን ታዲወስ››
‹‹አባትሽ ታዲወስ የታለ?››
👍65❤10👎1🔥1🤔1
‹‹እንዴ ይሄው፤ አታውቂውም እንዴ?›› በማለት ባላዋቂነቷ ሳቀችባት፡፡ ስለ እዚህ ልጅ ይበልጥ ለማወቅ በጣረች ቁጥር እየራቀባት መጣ‹‹ስንት እህቶች አሉሽ?››
<<አራት>>
‹‹ወንድሞችስ››
«አንድ»
<<እናታችሁስ>>
<< እናት የለንም፤ የሁላችንም ሞተዋል፡፡››
በዚህ ጊዜ አሮጊቷ በትሪ ሙሉ እንጀራ ቆልለው
ልሙጥ ሽሮ በላዩ ላይ ፈሰስ አድርገው ይዘው
በመምጣት መሀከል ላይ አስቀመጡ፡፡ልጆቹ
መብላት ጀመሩ ፡፡ እሷም ልክ እንደነሱ ለራሷም እየጎረሰች እነሱንም እያጎረሰች ተመሳሰለቻቸው፡፡ ያሮጊቷ ሽሮ እንደሚታየው
አይደለም፤ልዩ ጣዕም አለው፡፡ ከአስር አመት
በፊት የሞቱትን አያቷን አስታወሳት፡፡ እሳቸው
ነበሩ እንዲ አይነት ሽሮ ያበሏት የነበሩት፤ ከዛ
በኃላ ግን በአጋጣሚ እንኳን እንደዚህ አይነት ምግብ አግኝታ አታውቅም፡፡ ሆቴል
ከምትበላው ምግብ ጋር ሲነፃፀር ልዩነቱ የትየለሌ ቢሆንም ለእሷ ግን መሰጣት፡፡
ከጨረሱ በኃላ የምግብ ሂሳቡን ልትከፍል ስትል ቀድሟት ከፈለ ፡፡ስለፈራችው ብዙ
አልተከራከረችውም ፡፡ ከምግብ ቤቱ ወጡ…፡፡
‹‹ጨለማው ያስፈራል ልጆቹን ላስገባና እሸኝሻለሁ፡፡››
‹‹እሺ ››ብላ ተከለተለችው፡፡እንደቅድሙ ግን ከአጥሩ ውጭ ቆማ ልትጠብቀው
አልፈለገችም ፡፡ከልጆቹ ጋር ተጋፍታ ወደ ውስጥ ገባች፡፡ግቢው ሰፊ ነው፡፡ አምስት ሰርቪስ ቤቶችና አንድ በጣም ዘመናዊ የሆነ የተንጣለለ ቪላ ቤት አለ፡፡ ከሰርቪሶቹ ውስጥ አንዱን ተከራይቶ እንደሚኖር ገመተች፡፡ልጆቹ ግን ወደ ትልቁ ቤት እየተሯሯጡ ገቡ፡፡በረንዳ ላይ ሲደርሱ ቆመና << እንግዳዋን ሸኝቼያት መጣሁ እግራችሁን እየታጠባችሁ ጠብቁኝ›› ብሎ ፊቱን ሲያዞር እሷ ከህፃናቱ ጋር የቤቱን በራፍ አልፋ ወደ ውስጥ ገባች፡፡ ቤቱ ከስምንት በላይ ክፍሎች ከሰፊ ሳሎን ጋር ከነ ሙሉ ቤት ዕቃው አለው፡፡ ረጅሙ ሶፋ ላይ አንድ የአስር አመት ልጅ ፎጣ ለብሳ ተኝታለች፡፡
‹‹ቅር ካላለህ ትንሽ ብቆይ? ››አለችው፡፡
‹‹በንዴት ፊቱን እንዳጠቆረ ምንም ሳይመልስላት አልፎት ወደ አንደኛው ክፍል ሄደና ከፍቶ ገብቶ ዘጋው፡፡መኝታ ቤቱ እንደሆነ ገመተች፡፡
እሷም በቀስታ እርምጃ ወደ ተኛችው ልጅ በመሄድ ከጎኗ ሶፋው ላይ ተቀመጠች፡፡
‹‹ስምሽ ማነው?››
«ሠላም»
‹‹ሠላም ማን?››ተመሳሳይ መልስ መለሰችላት፡፡
‹‹ምንሽን ነው የሚያምሽ?››
‹‹እግሬን፡፡››
‹‹እኔ ዶክተር ነኝ፤ልይልሽ?››
‹‹እሺ›› ብላ ፈቀደችላት፡፡ቀስ ብላ የለበሰችውን ብርድ ልብስ ገልጣ ስታይ ዝግንን አላት፡፡ የልጅቷ ቀኝ እግር ጥምዝዝ ብሎ እንዳልሆነ ሆኗል ፡፡ ጣቶቿ አቅጣጫቸውን ለውጠው በተቃራኒው ናቸው ፡፡ግን አዲስ ጉዳት አይደለም፡፡እንደተጠማዘዘ የዳነና የቆየ ነው፡፡
‹‹ምን ሆነሽ ነው ሰላም?››
‹‹ልጅ ሆኜ አባቴ ነው እንዲህ ያደረገኝ፡፡››
ደነገጠች
‹‹ታዲዬስ ነው እንዲህ ያደረገሽ?››
‹‹ኧረ አይደለም ..አይደለም>>
ልጅቷ ተንገፈገፈች፡፡
‹‹አይ አባቴ ስላልሺኝ እኮ ነው፡፡››
‹‹ታዲያ ያ ክፉውን የድሮውን አባቴን ማለቴ ነዋ፡፡ሊለምንብኝ ነው እንዲህ ያበለሻሸኝ፡፡አሁን ግን የለም ታስሯል..ታዲ ነው ያሳሰረው፡፡››
‹‹አሁን ታዲያ እንዴት አመመሽ..አልዳነልሽም ነበር?>>
‹‹አይ ድኖልኛል ...ግን ሰሞኑን ወለም ስላለኝ ነው ህመሙ የተነሳብኝ፡፡››
‹‹እኔ ዶክተር ስለሆንኩ ነገ መድሀኒት ይዤልሽ መጣና ትድኚያለሽ እሺ፡፡››
‹‹ታዲ እኮ ሀኪም ቤት ወስዶኝ ነበር.፡፡ መድሀኒትም ተሰጥቶኛል፡፡››
‹‹አይ ጥሩ ነው››ብላ ትኩረቷን ወደ ሌሎቹ ልጆች ስትመለስ ተለቅ ተለቅ ያሉት የትናንሾቹን እግር እያጠቡ ተመለከተች፡፡
‹‹አንቺ የታዲዬስ ምኑ ነሽ?›› ጠየቀቻት ሰላም፡፡
‹‹ጓደኛው፡፡››
<<ጓደኛ እኮ የለውም፤አንቺን ከየት አገኘሽ?››
‹‹ብቻውን ነው እንዴ የሚኖረው?››ሚስት የለውም ወይ ለሚለው የውስጥ ጥያቄዋ መልስ ለማግኘት የተሰነዘረ ጥያቄ ነው፡፡
‹‹አይ አይደለም፤ከእኛ ጋር ነው ሚኖረው፡፡ ብታይ በጣም ነው የሚወደን ፡፡እኛም ውድድ ነው ምናደርገው፡፡››
ወሬዋን ሳትጨርስላት ታዲዬስ ከተከተተበት ክፍል ወጣ፡፡ ወደ ቴሌቨዥኑ ሄደና የህፃናት የካርቶን ፊልም ከፈተ ‹‹ፊልም እያያችሁ ጠብቁኝ ሸኚቼያት ልምጣ፡፡›› ሲላቸው ሁሉም በአንድነት ‹‹እሺ ታዲዬ›› አሉት ፡፡ ከተቀመጠችበት ፍራሽ ተነሳችና ሠላምን ግንባሯን ስማት ሌሎቹን ጉንጫቸውን በመሳም ተሰናብታቸው ወጣች፡፡የውጭ በራፉን ከፍተው እንደወጡ‹‹ታድለህ›› አለችው ምን ብላ ከእሱ ጋር ወሬ እንደምትጀምር ግራ ገብቷት፡፡
‹‹ለምኑ?>>
‹‹ልጆችህ በጣም ይወዱሀል፡፡››
‹‹እኔም በጣም እወዳቸዋለሁ፡፡››
‹‹ግን እነዚህን ሁሉ ህፃናት ያለእናት ማሳደግ በጣም አይከብድም?››
‹‹አይከብድም፡፡ልጆቹ የተንደላቀቀ የቅምጥል ኑሮ የለመዱ አይደሉም፡፡ ይህቺን ህይወት ሀ ብለው ሲጀምሩ በጣም ከከፋ እና ከዘቀጠ የድህነት መንደር ውስጥ ነው ፡፡እኔ ከእዛ ትንሽ የተሻለ ነገር ነው የማደርግላቸው፡፡ከበረንዳ ማደር ወደ ቤት ውስጥ፤ ጆንያ ከመልበስ ብርድልብስ ወደ መልበስ፤ ትርፍራፊ እና የተጣለ ምግብ ከመመገብ ልሙጥ ሽሮም ቢሆን መብላት... ይሄው ነው ብዙ አይጠይቁኝም፤ይሄንን ማድረግ ደግሞ አይከብደኝም፡፡››
‹‹ግን እኮ ብቻህን ከምትቸገር ብዙ በህፃናት ላይ የሚሰሩ እርዳታ ድርጅቶች አሉ ፤ኮምንኬት ብታደርጋቸው ይረዱሀል፡፡››
‹‹እኔ እርዳታ አልፈልግም ፡፡እነሱ ከፈለጉ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ህፃናት በየመንደሩ እና በየጎዳናው አሉ፡፡እነዚህ የእኔ ድርሻ ናቸው፡፡ ምን አልባት በምቾት እያኖርኳቸው መስሎ ያልተሰማሽ ከሆነ የተሳሳትሽ ይመስለኛል፡፡ እነዚህን ልጆች ግን ከምንም ነገር በላይ የሚርባቸው ፍቅር ነው፡፡ደግሞ እነዚህን ልጆች የማሳድጋቸው ደሀ ወይም ወላጅ አልባ
ስለሆኑ ከመሰለሽ ተሳስተሸል፡፡ሚጣ የኔ ልጅ ነች..ሌሎቹ አራቶቹ ደግሞ ወላጅ አልባ ብቻ ሳይሆኑ ጂኒዬሶችም ጭምር ናቸው..ለዛ ነው፡፡››
‹‹አልገባኝም፡፡››
‹‹ተይው በቀላሉ አይገባሽም፡፡››
እውነትም የዚህ ልጅ ነገር በቀላሉ አይገባም፡፡ ሊስትሮ እየሰሩ አምስት ልጆች በተንጣለለ ቪላ ቤት ውስጥ ማሳደግ፤ግራ የሚያጋባ ነገር ነው፡፡ወሬያቸውን እልባት ሳያበጁለት ዋናው አስፓልት ጋር ደርሱ፡፡
‹‹አሁን ታክሲ ወይም ባጃጅ ያዢና ወደ ሆቴልሽ ሂጂ፤እኔም ወደ ልጆቼ ልመለስ፡፡››
‹‹እሺ ስለ እራት ግብዣው አመሰግናለሁ፡፡ ልጆችህን ደግሞ በጣም ወድጄያቸዋለሁ፡፡ አንተም ጥሩ አባታቸው ብቻ ሳትሆን እናታቸውም ጭምር ነህ፡፡ደግሞ ቅድም የተናገርከው ልክ ነው ፤ ለሰው ልጅ ምግብ ብቻ ሳይሆን ፍቅርም መሰረታዊ ነገር ነው ፡፡›.ብላው ተሰናበተችው፡፡ እሱም ፊቱን አዙሮ ጉዞውን ቀጠለ፡፡ታዲዬስን እንዳገኘችው ለአንድ ወር ሙሉ በአዕምሮዋ ሲጉላላ የከረመውን ዕንቆቅልሽ በቀላሉ የምትፈታ መስሏት ነበር የተደሰተችው፡፡አሁን ግን ሌላ ተጨማሪ እንቆቅልሽ ጨምራ በመብሰልሰል ወደ ክፍሏ ተመለሰች፡፡
✨ይቀጥላል✨
አሁንም ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ #Share እያደረጋቹ ቤተሰቦች በቅንነት እባካቹ👍
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
<<አራት>>
‹‹ወንድሞችስ››
«አንድ»
<<እናታችሁስ>>
<< እናት የለንም፤ የሁላችንም ሞተዋል፡፡››
በዚህ ጊዜ አሮጊቷ በትሪ ሙሉ እንጀራ ቆልለው
ልሙጥ ሽሮ በላዩ ላይ ፈሰስ አድርገው ይዘው
በመምጣት መሀከል ላይ አስቀመጡ፡፡ልጆቹ
መብላት ጀመሩ ፡፡ እሷም ልክ እንደነሱ ለራሷም እየጎረሰች እነሱንም እያጎረሰች ተመሳሰለቻቸው፡፡ ያሮጊቷ ሽሮ እንደሚታየው
አይደለም፤ልዩ ጣዕም አለው፡፡ ከአስር አመት
በፊት የሞቱትን አያቷን አስታወሳት፡፡ እሳቸው
ነበሩ እንዲ አይነት ሽሮ ያበሏት የነበሩት፤ ከዛ
በኃላ ግን በአጋጣሚ እንኳን እንደዚህ አይነት ምግብ አግኝታ አታውቅም፡፡ ሆቴል
ከምትበላው ምግብ ጋር ሲነፃፀር ልዩነቱ የትየለሌ ቢሆንም ለእሷ ግን መሰጣት፡፡
ከጨረሱ በኃላ የምግብ ሂሳቡን ልትከፍል ስትል ቀድሟት ከፈለ ፡፡ስለፈራችው ብዙ
አልተከራከረችውም ፡፡ ከምግብ ቤቱ ወጡ…፡፡
‹‹ጨለማው ያስፈራል ልጆቹን ላስገባና እሸኝሻለሁ፡፡››
‹‹እሺ ››ብላ ተከለተለችው፡፡እንደቅድሙ ግን ከአጥሩ ውጭ ቆማ ልትጠብቀው
አልፈለገችም ፡፡ከልጆቹ ጋር ተጋፍታ ወደ ውስጥ ገባች፡፡ግቢው ሰፊ ነው፡፡ አምስት ሰርቪስ ቤቶችና አንድ በጣም ዘመናዊ የሆነ የተንጣለለ ቪላ ቤት አለ፡፡ ከሰርቪሶቹ ውስጥ አንዱን ተከራይቶ እንደሚኖር ገመተች፡፡ልጆቹ ግን ወደ ትልቁ ቤት እየተሯሯጡ ገቡ፡፡በረንዳ ላይ ሲደርሱ ቆመና << እንግዳዋን ሸኝቼያት መጣሁ እግራችሁን እየታጠባችሁ ጠብቁኝ›› ብሎ ፊቱን ሲያዞር እሷ ከህፃናቱ ጋር የቤቱን በራፍ አልፋ ወደ ውስጥ ገባች፡፡ ቤቱ ከስምንት በላይ ክፍሎች ከሰፊ ሳሎን ጋር ከነ ሙሉ ቤት ዕቃው አለው፡፡ ረጅሙ ሶፋ ላይ አንድ የአስር አመት ልጅ ፎጣ ለብሳ ተኝታለች፡፡
‹‹ቅር ካላለህ ትንሽ ብቆይ? ››አለችው፡፡
‹‹በንዴት ፊቱን እንዳጠቆረ ምንም ሳይመልስላት አልፎት ወደ አንደኛው ክፍል ሄደና ከፍቶ ገብቶ ዘጋው፡፡መኝታ ቤቱ እንደሆነ ገመተች፡፡
እሷም በቀስታ እርምጃ ወደ ተኛችው ልጅ በመሄድ ከጎኗ ሶፋው ላይ ተቀመጠች፡፡
‹‹ስምሽ ማነው?››
«ሠላም»
‹‹ሠላም ማን?››ተመሳሳይ መልስ መለሰችላት፡፡
‹‹ምንሽን ነው የሚያምሽ?››
‹‹እግሬን፡፡››
‹‹እኔ ዶክተር ነኝ፤ልይልሽ?››
‹‹እሺ›› ብላ ፈቀደችላት፡፡ቀስ ብላ የለበሰችውን ብርድ ልብስ ገልጣ ስታይ ዝግንን አላት፡፡ የልጅቷ ቀኝ እግር ጥምዝዝ ብሎ እንዳልሆነ ሆኗል ፡፡ ጣቶቿ አቅጣጫቸውን ለውጠው በተቃራኒው ናቸው ፡፡ግን አዲስ ጉዳት አይደለም፡፡እንደተጠማዘዘ የዳነና የቆየ ነው፡፡
‹‹ምን ሆነሽ ነው ሰላም?››
‹‹ልጅ ሆኜ አባቴ ነው እንዲህ ያደረገኝ፡፡››
ደነገጠች
‹‹ታዲዬስ ነው እንዲህ ያደረገሽ?››
‹‹ኧረ አይደለም ..አይደለም>>
ልጅቷ ተንገፈገፈች፡፡
‹‹አይ አባቴ ስላልሺኝ እኮ ነው፡፡››
‹‹ታዲያ ያ ክፉውን የድሮውን አባቴን ማለቴ ነዋ፡፡ሊለምንብኝ ነው እንዲህ ያበለሻሸኝ፡፡አሁን ግን የለም ታስሯል..ታዲ ነው ያሳሰረው፡፡››
‹‹አሁን ታዲያ እንዴት አመመሽ..አልዳነልሽም ነበር?>>
‹‹አይ ድኖልኛል ...ግን ሰሞኑን ወለም ስላለኝ ነው ህመሙ የተነሳብኝ፡፡››
‹‹እኔ ዶክተር ስለሆንኩ ነገ መድሀኒት ይዤልሽ መጣና ትድኚያለሽ እሺ፡፡››
‹‹ታዲ እኮ ሀኪም ቤት ወስዶኝ ነበር.፡፡ መድሀኒትም ተሰጥቶኛል፡፡››
‹‹አይ ጥሩ ነው››ብላ ትኩረቷን ወደ ሌሎቹ ልጆች ስትመለስ ተለቅ ተለቅ ያሉት የትናንሾቹን እግር እያጠቡ ተመለከተች፡፡
‹‹አንቺ የታዲዬስ ምኑ ነሽ?›› ጠየቀቻት ሰላም፡፡
‹‹ጓደኛው፡፡››
<<ጓደኛ እኮ የለውም፤አንቺን ከየት አገኘሽ?››
‹‹ብቻውን ነው እንዴ የሚኖረው?››ሚስት የለውም ወይ ለሚለው የውስጥ ጥያቄዋ መልስ ለማግኘት የተሰነዘረ ጥያቄ ነው፡፡
‹‹አይ አይደለም፤ከእኛ ጋር ነው ሚኖረው፡፡ ብታይ በጣም ነው የሚወደን ፡፡እኛም ውድድ ነው ምናደርገው፡፡››
ወሬዋን ሳትጨርስላት ታዲዬስ ከተከተተበት ክፍል ወጣ፡፡ ወደ ቴሌቨዥኑ ሄደና የህፃናት የካርቶን ፊልም ከፈተ ‹‹ፊልም እያያችሁ ጠብቁኝ ሸኚቼያት ልምጣ፡፡›› ሲላቸው ሁሉም በአንድነት ‹‹እሺ ታዲዬ›› አሉት ፡፡ ከተቀመጠችበት ፍራሽ ተነሳችና ሠላምን ግንባሯን ስማት ሌሎቹን ጉንጫቸውን በመሳም ተሰናብታቸው ወጣች፡፡የውጭ በራፉን ከፍተው እንደወጡ‹‹ታድለህ›› አለችው ምን ብላ ከእሱ ጋር ወሬ እንደምትጀምር ግራ ገብቷት፡፡
‹‹ለምኑ?>>
‹‹ልጆችህ በጣም ይወዱሀል፡፡››
‹‹እኔም በጣም እወዳቸዋለሁ፡፡››
‹‹ግን እነዚህን ሁሉ ህፃናት ያለእናት ማሳደግ በጣም አይከብድም?››
‹‹አይከብድም፡፡ልጆቹ የተንደላቀቀ የቅምጥል ኑሮ የለመዱ አይደሉም፡፡ ይህቺን ህይወት ሀ ብለው ሲጀምሩ በጣም ከከፋ እና ከዘቀጠ የድህነት መንደር ውስጥ ነው ፡፡እኔ ከእዛ ትንሽ የተሻለ ነገር ነው የማደርግላቸው፡፡ከበረንዳ ማደር ወደ ቤት ውስጥ፤ ጆንያ ከመልበስ ብርድልብስ ወደ መልበስ፤ ትርፍራፊ እና የተጣለ ምግብ ከመመገብ ልሙጥ ሽሮም ቢሆን መብላት... ይሄው ነው ብዙ አይጠይቁኝም፤ይሄንን ማድረግ ደግሞ አይከብደኝም፡፡››
‹‹ግን እኮ ብቻህን ከምትቸገር ብዙ በህፃናት ላይ የሚሰሩ እርዳታ ድርጅቶች አሉ ፤ኮምንኬት ብታደርጋቸው ይረዱሀል፡፡››
‹‹እኔ እርዳታ አልፈልግም ፡፡እነሱ ከፈለጉ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ህፃናት በየመንደሩ እና በየጎዳናው አሉ፡፡እነዚህ የእኔ ድርሻ ናቸው፡፡ ምን አልባት በምቾት እያኖርኳቸው መስሎ ያልተሰማሽ ከሆነ የተሳሳትሽ ይመስለኛል፡፡ እነዚህን ልጆች ግን ከምንም ነገር በላይ የሚርባቸው ፍቅር ነው፡፡ደግሞ እነዚህን ልጆች የማሳድጋቸው ደሀ ወይም ወላጅ አልባ
ስለሆኑ ከመሰለሽ ተሳስተሸል፡፡ሚጣ የኔ ልጅ ነች..ሌሎቹ አራቶቹ ደግሞ ወላጅ አልባ ብቻ ሳይሆኑ ጂኒዬሶችም ጭምር ናቸው..ለዛ ነው፡፡››
‹‹አልገባኝም፡፡››
‹‹ተይው በቀላሉ አይገባሽም፡፡››
እውነትም የዚህ ልጅ ነገር በቀላሉ አይገባም፡፡ ሊስትሮ እየሰሩ አምስት ልጆች በተንጣለለ ቪላ ቤት ውስጥ ማሳደግ፤ግራ የሚያጋባ ነገር ነው፡፡ወሬያቸውን እልባት ሳያበጁለት ዋናው አስፓልት ጋር ደርሱ፡፡
‹‹አሁን ታክሲ ወይም ባጃጅ ያዢና ወደ ሆቴልሽ ሂጂ፤እኔም ወደ ልጆቼ ልመለስ፡፡››
‹‹እሺ ስለ እራት ግብዣው አመሰግናለሁ፡፡ ልጆችህን ደግሞ በጣም ወድጄያቸዋለሁ፡፡ አንተም ጥሩ አባታቸው ብቻ ሳትሆን እናታቸውም ጭምር ነህ፡፡ደግሞ ቅድም የተናገርከው ልክ ነው ፤ ለሰው ልጅ ምግብ ብቻ ሳይሆን ፍቅርም መሰረታዊ ነገር ነው ፡፡›.ብላው ተሰናበተችው፡፡ እሱም ፊቱን አዙሮ ጉዞውን ቀጠለ፡፡ታዲዬስን እንዳገኘችው ለአንድ ወር ሙሉ በአዕምሮዋ ሲጉላላ የከረመውን ዕንቆቅልሽ በቀላሉ የምትፈታ መስሏት ነበር የተደሰተችው፡፡አሁን ግን ሌላ ተጨማሪ እንቆቅልሽ ጨምራ በመብሰልሰል ወደ ክፍሏ ተመለሰች፡፡
✨ይቀጥላል✨
አሁንም ዩቲዩብ ቻናል #ሰብስክራይብ #Share እያደረጋቹ ቤተሰቦች በቅንነት እባካቹ👍
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍88❤12😁4👎1🥰1
#ወዳጄ_ሆይ!
🌟ሰውን የሚያስከብረው ጌጣጌጥ ነው ብለህ ጌጥ አታብዛ።የሰው ልጅ ክብሩ እውነተኛ ቃሉ እና ቅንነቱ መሆኑን ተረዳ ።
#ወዳጄ_ሆይ!
🌟ተማረ ተመራመረ ብለህ ሰውን አታድንቀው ።ምንም ቢያውቅ ቢራቀቅ የሞቱን ቀን
አያውቅም ብለህ እዘንለት
#ወዳጄ_ሆይ!
🌟የጋለ ምጣድ አትንካ ትቃጠላለህ።በስሜት ያበደን ሰው እይዛለሁ አትበል ታዝናለህ።
#ወዳጄ_ሆይ!
🌟መንፈሳቸው እንደ ብረት ከቀዘቀዘባቸው ስዎች ጋር መኖር በጣም ከባድ ነው።አንተ እነርሱን
እስክታሞቅ እነርሱ አንተን ያበርዱሀልና ተጠንቀቅ ።
#ወዳጄ_ሆይ!
🌟ፈረስ የፈለግበት ድረስ ያድርስህ እንጂ ፈረሱ የፈለገበት አትድረስ ። እንዲሁም ፍቅር
በሚመስል ነገር ስክረህ በከንቱዎች ምክር አትራመድ ።
#ወዳጄ_ሆይ!
🌟መስማትና መስማማት ይለያያልና የስማህ ሁሉ የተስማማ መስሎህ አትዘናጋ ።
መስማማት ማድረግ ነውና የተስማማ ስውን በተግባር ታየዋለህ። ስዎች በጆሮ ሲስሙህ
ራሳቸውን ይነቀንቃሉ በልባቸው ሲያዳምጡህ ግን ከቀድሞ ስህተታቸዉ ይርቃሉ ::ይለወጣሉ::
ተረድተውሀላ!!
#ወዳጄ_ሆይ!
🌟ንግግርህ ፣አስተሳስብህን ፣ኑሮህን የምትመራበትን መመሪያህን ማሳያህ ነውና ንግግርህን በማስተዋል አድርገው
አፍና በራፍ እኩል ይከፈታል።❤️
ቤተሰቦች የዩቲዩብ ቻናሉን #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ እንጂ ለ500 እኮ ትንሽ ነው የቀረው እባካቹ ቤተሰቦች
ሰብስክረይብ እያረጋቹ ያደረጋችሁ ደግሞ ሌሎች እዲያደርጉ #Share እያደረጋቹ አመሰግናለሁ፡፡
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
🌟ሰውን የሚያስከብረው ጌጣጌጥ ነው ብለህ ጌጥ አታብዛ።የሰው ልጅ ክብሩ እውነተኛ ቃሉ እና ቅንነቱ መሆኑን ተረዳ ።
#ወዳጄ_ሆይ!
🌟ተማረ ተመራመረ ብለህ ሰውን አታድንቀው ።ምንም ቢያውቅ ቢራቀቅ የሞቱን ቀን
አያውቅም ብለህ እዘንለት
#ወዳጄ_ሆይ!
🌟የጋለ ምጣድ አትንካ ትቃጠላለህ።በስሜት ያበደን ሰው እይዛለሁ አትበል ታዝናለህ።
#ወዳጄ_ሆይ!
🌟መንፈሳቸው እንደ ብረት ከቀዘቀዘባቸው ስዎች ጋር መኖር በጣም ከባድ ነው።አንተ እነርሱን
እስክታሞቅ እነርሱ አንተን ያበርዱሀልና ተጠንቀቅ ።
#ወዳጄ_ሆይ!
🌟ፈረስ የፈለግበት ድረስ ያድርስህ እንጂ ፈረሱ የፈለገበት አትድረስ ። እንዲሁም ፍቅር
በሚመስል ነገር ስክረህ በከንቱዎች ምክር አትራመድ ።
#ወዳጄ_ሆይ!
🌟መስማትና መስማማት ይለያያልና የስማህ ሁሉ የተስማማ መስሎህ አትዘናጋ ።
መስማማት ማድረግ ነውና የተስማማ ስውን በተግባር ታየዋለህ። ስዎች በጆሮ ሲስሙህ
ራሳቸውን ይነቀንቃሉ በልባቸው ሲያዳምጡህ ግን ከቀድሞ ስህተታቸዉ ይርቃሉ ::ይለወጣሉ::
ተረድተውሀላ!!
#ወዳጄ_ሆይ!
🌟ንግግርህ ፣አስተሳስብህን ፣ኑሮህን የምትመራበትን መመሪያህን ማሳያህ ነውና ንግግርህን በማስተዋል አድርገው
አፍና በራፍ እኩል ይከፈታል።❤️
ቤተሰቦች የዩቲዩብ ቻናሉን #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ እንጂ ለ500 እኮ ትንሽ ነው የቀረው እባካቹ ቤተሰቦች
ሰብስክረይብ እያረጋቹ ያደረጋችሁ ደግሞ ሌሎች እዲያደርጉ #Share እያደረጋቹ አመሰግናለሁ፡፡
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍28👏18❤6🥰1
#ትንግርት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ዶ/ር ሶፊያ በማግስቱ ከምሽቱ 12፡3ዐ ላይ መኪናዋን እያሽከረከረች ታዲዮስ ቤት ደረሰች፡፡ሦስት ኩርቱ ፔስታል ሙሉ ስጦታ ይዛለች ፤ለአምስቱም ልጆች ፡፡በመከራ እየተንገዳገደች ነበር ዕቃዎቹን ተሸክማ በረንዳው ላይ ማድረስ የቻለችው፡፡መሬት አስቀመጠችውና በራፉን አንኳኳች፡፡ ሃያ አምስት ዓመት የሚሆነው ባለ ሹሩባ ፀጉር መልከ መልካም ወጣት ከፈተላት፡፡
‹‹አቤት ምን ነበር?››ዓይኑ ያልተለመደ ነገር በማየቱ የመገረም ፊት እያሳያት፡፡
‹‹ታዲዬስን ፈልጌው ነበር፡፡››
‹‹ይቅርታ ታዲ ከአንድ ሰዓት በኃላ ነው የሚመጣው፡፡››
<< አመጣጤማ ሰላምን ልጠይቃት ነበር፤የታዲ ዘመድ ነኝ፤ማታ እዚህ በነበርኩበት ሰዓት የሰላምን መታመም አይቼ ስለነበር አሳስቦኝ ነው፡፡››
ፈራ ተባ እያለ በራፉን በሰፊው ከፈተላት እና አንዱን ፔስታል ለእሷ ትቶ ሁለቱን ወደ ሳሎን ውስጥ በማስገባት ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠላት‹‹እህት .. እንግዲህ አረፍ በይ ትንሽ ስራ ላይ ነን፡፡ ››ብሏት ጥሏት ሄደና በመደዳ ካሉት ክፍሎች መሀከል ወደ መጀመሪያው ክፍል ገባ፡፡ ሶፋው ላይ ቁጭ አለች፡፡ልጁ ከገባበት ክፍል አካባቢ የፒያኖ ድምፅ ይሰማታል፤የሚመስጥ ክላሲካል ሙዚቃ፡፡ዝም ብላ በደመነፍስ ባዶውን ሳሎን ለቃ የሙዚቃውን ድምፅ ተከትላ ወደ ክፍሎቹ መራመድ ጀመረች፡፡የመጀመሪያው ክፍል በራፍ አጠገብ ስትደርስ እርምጃዋን ገታችና ቆመች፡፡በራፉ ገርበብ ብሎ ስለነበር አንገቷን አሰገገች፡፡
እንደመጣች በራፉን የከፈተላትን ልጅ ሹሩባ ቀድሞ ታያት፡፡ይበልጥ ስትጠጋ ሠላምን አየቻት፡፡ በሹክሹክታ ወደ ውስጥ ዘልቃ ገባች፡፡ሠላም ወንበር ላይ ቁጭ ብላለች፡፡ ከፊቷ የስዕል ሸራ ተወጥሮላት ፊቷ በቀረበላት የተዘበራረቀ ቀለም በቀጫጫ እጆቿ የያዘችውን ብሩሽ እያጠቀሰች የሆነ ስዕል ትስላለች፡፡ወጣቱ ቀና ብሎ ሶፊያን ተመለከታትና መልሶ ቀልቡን ሰላም ወደምትስለው ስዕል መለሰ፡፡ ልትረብሻቸው ስላልፈለገች ክፍሉን በቀስታ ለቃ ወጣች፡፡
ወደ ሳሎን ልትመለስ ካሰበች በኃላ የፒያኖው ድምፅ የሚንቆረቆረው ከሚቀጥለው ክፍል እንደሆነ ስታውቅ ሀሳቧን ቀየረችና ወደዛው አመራች፡፡ገርበብ ያለውን ክፍል በተመሳሳይ ገፋ አድርጋ ወደ ውስጥ ገባች፡፡ መሀከል ወለል ላይ አንድ መለስተኛ ፒያኖ ተመለከተች፡፡ አንድ ወጣት ግን አይነስውር የሆነች ምታምር ሴት ሁለቱን ሴት ህፃናት ተራ በተራ ጣታቸውን እየያዘች ታለማምዳቸዋለች፡፡ ግድግዳውን ተደግፋ በተመስጦ ትከታተላቸው
ጀመር፡፡ከአስር ደቂቃ ቆይታ በኃላ ዓይነ ስውሯ
አስተማሪ አዳምጡ አለቻቸውና ሁለቱን ሴት
ልጆች መቀመጫቸውን ይዘው እንዲቀመጡ
በማድረግ ጣቶቾን ፒያኖው ላይ ማርመስመስ ጀመረች፡፡ልጆቹ ብቻ ሳይሆኑ ዶ/ር ሶፊያም
ድንዝዝ ብላ ነው የተከታተለቻችው፡፡እሷ
እራሷም ከሙዚቃው ስልት ጋር ከወዲህ ወዲህ አንገቷን ስታወናጭፍ እረጅም ጥቁር ፀጉሯ በአየሩ ላይ ይበተናል፡፡የተመልካች ልብን
ስልብ ያደርጋል ፡፡ስትጨርስና ጣቶቾን
ስትሰበስብ ሳታስበው አጨበጨበችላት፡፡
ሁለቱም ህፃናት ልጆቹ እያቀፋ በመሳም
ፍቅራቸውን ገለፁላት፡፡
ሄለን ‹‹ፅዬንዬ እኔም ሳድግ እንደአንቺ መጫወት እፈልጋለሁ፡፡አንቺን መሆን ነው የምፈልገው፡፡››አለቻት፡፡
ፅዬን በግምት እጇን ወደ እሷ ላከቻና የለበሰችውን ጃኬት ይዛ ወደ ራሷ ጎትታት ጉያዋ ውስጥ ሸጉጣ አቀፈቻት ‹‹በቅርብ ቀን
እንደ እኔ ብቻ ሳይሆን ከእኔም በላይ ትጫወቺያለሽ፡፡ አንቺ ምርጥ ሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋች ሀሊማ ደግሞ ምርጥ ድምፃዊ እንደምትሆኑ እርግጠኛ ነኝ፡፡››ብላ በማበረታታት ጉንጯን ሳመቻት፡፡
ዶ/ር ሶፊያ ቀስ ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣችና ሶስተኛው ክፍል ገባች፡፡ አንድ የአስራ ስምንት አመት ወጣት ሴት የአማርኛ ፊደል ተራ በተራ ብላክ ቦርድ ላይ እየፃፉች ሚጣን እያስተማረቻት ነው፡፡
እስከአሁን ያላየችው ወንዱን ልጅ ብቻ ነው፡፡ እሱ አራተኛው ክፍል ውስጥ ይሆናል›› ስትል ገመተች‹‹ለመሆኑ እሱስ ምን እየተማረ ይሆን?›› ለማወቅ በጣም ጓጓች.. ወደ አራተኛ ክፍል አመራች ፡፡እስከአሁን ካየቻቸው ሶስቱም ክፍሎች በተሻለ ይሄኛው በእጥፍ ሰፋት አለው፡፡ ግን ቤት ሳይሆን ኳተት ማጠራቀሚያ ክፍል ነው ማለት ይቻላል፡፡በኤሌክትሮኒክ ዕቃዎች፣በብረታ ብረት ቁርጥራጮች፣በተበላሹ ቴሌቨዢኖች፣ሬዲዬኖች
ገመዳ ገመዶች ተሞልቷል፡፡ዕድሜው ከ1ዐ የማይበልጠው የሰውነቱ ግዙፍነት ግን የ15 ዓመት ታዳጊ የሚያስመስለው ድንቡሽቡሽ ልጁ ኮተቶቹ መሀከል ወለል ላይ ተዘርፍጦ ላፕቶፕ ኮምፒተር ላይ አፍጥጧል፡፡ድምፅ ብታሰማውም ሊሰማት አልቻለም፡፡ሹክክ ብላ ወጥታ ወደ ሳሎን ተመለሰች እና ስላየችው ነገር በግርምት ማሰላሰል ጀመረች፡፡
አንድ ሰዓት ሲሆን ሁሉም የእለት ስራቸውን አጠናቀው ከየአስተማሪዎቻቸው ጋር ከየክፍላቸው ወጡ፤ ከወንድዬው ልጅ በስተቀር፡፡ ሠላምንም አስተማሪዋ ደግፎት አመጣትና ከእሷ ጐን እንድትቀመጥ ከረዳት በኃላ‹‹ይቅርታ ቅድም በስራ መሀል ስለነበርኩ በቅጡ አላናገርኩሽም…የቤቱ ህግ ነው፡፡ ከሁሉ በፊት ስራ ይቀድማል፡፡አላዛር እባላለሁ፡፡››በማለት እጁን ለሰላምታ ዘረጋላት፡፡ እሷም እየጨበጠችው‹‹ሶፊያ እባላለሁ›› አለችው፡፡
‹‹አሁን ሠላምን መጠየቅ ትችያለሽ..ያው ከጎንሽ አስቀምጪልሻለሁ፡፡ እኔ ሽንት ቤት ደርሼ መጣው›› ብሎ ወደ ጓሮ ሄደ ::
‹‹አመሰግናለሁ››ብላው የሰላምን ግንባሯን ሳመቻት፡፡
‹‹ትመጪያለሽ ብዬ ስጠብቅሽ ነበር ::>> አለቻት ሠላም በመምጣቷ መደሰቷን በፈገግታዋ እያረጋገጠችላት፡፡
‹‹ይሄው መጣሁልሽ፤ ለመሆኑ የሚያምሽ ተሻለሽ?»
‹‹አዎ ...ዛሬ ሚጠዘጥዘኝ ትቶኛል፡፡››
‹‹አይ ጥሩ ነው፡፡››ንግግሯን ሳትጨርስ ሌሎቹ ልጆች ከያሉበት መጥተው ወረሯት ፡፡ግማሹ ግንባሯን ግማሹ ጉንጮን ሳሟት፡፡እሷም በየተራ ሳመቻቸው፡፡ለሚያያቸው ዕውቂያቸው የአንድ ቀን ብቻ አይመስልም፡፡
አላዛር ከጓሮ ተመለሰና ከሚጠብቁት ጓደኞቹ ጋር ከተቀላቀለ በኃላ ድምፅን ከፍ አድርጐ << ሶፊ ልንሄድ ነው››ሲላት ልጆቹን ‹‹ቆይ አንዴ መጣሁ >>ብላ ከተቀመጠችበት ተነሳችና ወደ እነ አላዛር ሄደች፡፡
‹‹ይቅርታ እኔ የታዲ ዘመድ ነኝ፤ ከሁላችሁም ጋር ብተዋወቅ ደስ ይለኛል፡፡››
አይነስውሯ ቀድማ ለሰላምታ እጇን እየዘረጋችላት‹‹ፅዬን እባላለሁ›› አለቻት፡፡
‹‹ዶ/ር ሶፍያና፡፡››
‹‹ቤቲ..ቤተልሄም፡፡›› እባላለሁ..ሌላዋ ቀጠለች፡፡
አላዛር መሀል ገብቶ ማብራሪያ በመስጠት ቀጠለ ‹‹...ፂ እንዳየሻት አሪፍ የሙዚቃ ሰው ነች፡፡ጊታር እና ፒያኖ ነፍስ አድርጋ ትጫወታለች፡፡የያሬድ ግርፋ ነች፤ በሞያዋ የሙዚቃ አስተማሪ ነች፡፡እዚህም እንዳየሻት የሄለን እና የሚኪያ የሙዚቃ አስተማሪ ነች፡፡…
ቤቲ ደግሞ ሀይ‐ስኩል አማርኛ ቲቸር ነች፡፡
የስድስት ኪሎ ምሩቅ ነች፡፡እዚህ ያሉትን ህፃናት አማርኛም ሆነ እንግሊዘኛ ቋንቋ በፕሮግራም
ታስተምራቸዋለች፡፡አንዳንዴ
ሂሳብም ቀልቀል ለማድረግ ትሞክራለች ግን ቀሺም ነች፡፡ሂሳብ እና ጠቅላላ ዕውቀትን በተመለከተ ጂኒዬሱ ነው የሚያስተምራቸው፡፡
ጂኒዬሱ ስል ታዲዬስን ማለቴ ነው፡፡እኔ ያው
እዚህ ቤት የቀለም ሽታ የምትወድ አንድ ሰላም
የምትባል ልዩ ነፍስ ያላት ልጅ አለች ፤እሷን ስዕል አስተምራታለሁ፡፡አስተምራታለሁ ማለት
እንኳን ይከብዳል ስትስል
አያታለው፤የምትፈልገውን ቁሳቁስ አቀብላታለው ማለቱ ነው የሚሻለው ፡፡
ምክንያቱም አሁን ባለንበት ሁኔታ ችሎታችን እኩል ነው፤ከስድስት ወር በኃላ ደግሞ እኔ ቁጭ ብዬ ከእሷ መማሬ አይቀርም፡፡››
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
ዶ/ር ሶፊያ በማግስቱ ከምሽቱ 12፡3ዐ ላይ መኪናዋን እያሽከረከረች ታዲዮስ ቤት ደረሰች፡፡ሦስት ኩርቱ ፔስታል ሙሉ ስጦታ ይዛለች ፤ለአምስቱም ልጆች ፡፡በመከራ እየተንገዳገደች ነበር ዕቃዎቹን ተሸክማ በረንዳው ላይ ማድረስ የቻለችው፡፡መሬት አስቀመጠችውና በራፉን አንኳኳች፡፡ ሃያ አምስት ዓመት የሚሆነው ባለ ሹሩባ ፀጉር መልከ መልካም ወጣት ከፈተላት፡፡
‹‹አቤት ምን ነበር?››ዓይኑ ያልተለመደ ነገር በማየቱ የመገረም ፊት እያሳያት፡፡
‹‹ታዲዬስን ፈልጌው ነበር፡፡››
‹‹ይቅርታ ታዲ ከአንድ ሰዓት በኃላ ነው የሚመጣው፡፡››
<< አመጣጤማ ሰላምን ልጠይቃት ነበር፤የታዲ ዘመድ ነኝ፤ማታ እዚህ በነበርኩበት ሰዓት የሰላምን መታመም አይቼ ስለነበር አሳስቦኝ ነው፡፡››
ፈራ ተባ እያለ በራፉን በሰፊው ከፈተላት እና አንዱን ፔስታል ለእሷ ትቶ ሁለቱን ወደ ሳሎን ውስጥ በማስገባት ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠላት‹‹እህት .. እንግዲህ አረፍ በይ ትንሽ ስራ ላይ ነን፡፡ ››ብሏት ጥሏት ሄደና በመደዳ ካሉት ክፍሎች መሀከል ወደ መጀመሪያው ክፍል ገባ፡፡ ሶፋው ላይ ቁጭ አለች፡፡ልጁ ከገባበት ክፍል አካባቢ የፒያኖ ድምፅ ይሰማታል፤የሚመስጥ ክላሲካል ሙዚቃ፡፡ዝም ብላ በደመነፍስ ባዶውን ሳሎን ለቃ የሙዚቃውን ድምፅ ተከትላ ወደ ክፍሎቹ መራመድ ጀመረች፡፡የመጀመሪያው ክፍል በራፍ አጠገብ ስትደርስ እርምጃዋን ገታችና ቆመች፡፡በራፉ ገርበብ ብሎ ስለነበር አንገቷን አሰገገች፡፡
እንደመጣች በራፉን የከፈተላትን ልጅ ሹሩባ ቀድሞ ታያት፡፡ይበልጥ ስትጠጋ ሠላምን አየቻት፡፡ በሹክሹክታ ወደ ውስጥ ዘልቃ ገባች፡፡ሠላም ወንበር ላይ ቁጭ ብላለች፡፡ ከፊቷ የስዕል ሸራ ተወጥሮላት ፊቷ በቀረበላት የተዘበራረቀ ቀለም በቀጫጫ እጆቿ የያዘችውን ብሩሽ እያጠቀሰች የሆነ ስዕል ትስላለች፡፡ወጣቱ ቀና ብሎ ሶፊያን ተመለከታትና መልሶ ቀልቡን ሰላም ወደምትስለው ስዕል መለሰ፡፡ ልትረብሻቸው ስላልፈለገች ክፍሉን በቀስታ ለቃ ወጣች፡፡
ወደ ሳሎን ልትመለስ ካሰበች በኃላ የፒያኖው ድምፅ የሚንቆረቆረው ከሚቀጥለው ክፍል እንደሆነ ስታውቅ ሀሳቧን ቀየረችና ወደዛው አመራች፡፡ገርበብ ያለውን ክፍል በተመሳሳይ ገፋ አድርጋ ወደ ውስጥ ገባች፡፡ መሀከል ወለል ላይ አንድ መለስተኛ ፒያኖ ተመለከተች፡፡ አንድ ወጣት ግን አይነስውር የሆነች ምታምር ሴት ሁለቱን ሴት ህፃናት ተራ በተራ ጣታቸውን እየያዘች ታለማምዳቸዋለች፡፡ ግድግዳውን ተደግፋ በተመስጦ ትከታተላቸው
ጀመር፡፡ከአስር ደቂቃ ቆይታ በኃላ ዓይነ ስውሯ
አስተማሪ አዳምጡ አለቻቸውና ሁለቱን ሴት
ልጆች መቀመጫቸውን ይዘው እንዲቀመጡ
በማድረግ ጣቶቾን ፒያኖው ላይ ማርመስመስ ጀመረች፡፡ልጆቹ ብቻ ሳይሆኑ ዶ/ር ሶፊያም
ድንዝዝ ብላ ነው የተከታተለቻችው፡፡እሷ
እራሷም ከሙዚቃው ስልት ጋር ከወዲህ ወዲህ አንገቷን ስታወናጭፍ እረጅም ጥቁር ፀጉሯ በአየሩ ላይ ይበተናል፡፡የተመልካች ልብን
ስልብ ያደርጋል ፡፡ስትጨርስና ጣቶቾን
ስትሰበስብ ሳታስበው አጨበጨበችላት፡፡
ሁለቱም ህፃናት ልጆቹ እያቀፋ በመሳም
ፍቅራቸውን ገለፁላት፡፡
ሄለን ‹‹ፅዬንዬ እኔም ሳድግ እንደአንቺ መጫወት እፈልጋለሁ፡፡አንቺን መሆን ነው የምፈልገው፡፡››አለቻት፡፡
ፅዬን በግምት እጇን ወደ እሷ ላከቻና የለበሰችውን ጃኬት ይዛ ወደ ራሷ ጎትታት ጉያዋ ውስጥ ሸጉጣ አቀፈቻት ‹‹በቅርብ ቀን
እንደ እኔ ብቻ ሳይሆን ከእኔም በላይ ትጫወቺያለሽ፡፡ አንቺ ምርጥ ሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋች ሀሊማ ደግሞ ምርጥ ድምፃዊ እንደምትሆኑ እርግጠኛ ነኝ፡፡››ብላ በማበረታታት ጉንጯን ሳመቻት፡፡
ዶ/ር ሶፊያ ቀስ ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣችና ሶስተኛው ክፍል ገባች፡፡ አንድ የአስራ ስምንት አመት ወጣት ሴት የአማርኛ ፊደል ተራ በተራ ብላክ ቦርድ ላይ እየፃፉች ሚጣን እያስተማረቻት ነው፡፡
እስከአሁን ያላየችው ወንዱን ልጅ ብቻ ነው፡፡ እሱ አራተኛው ክፍል ውስጥ ይሆናል›› ስትል ገመተች‹‹ለመሆኑ እሱስ ምን እየተማረ ይሆን?›› ለማወቅ በጣም ጓጓች.. ወደ አራተኛ ክፍል አመራች ፡፡እስከአሁን ካየቻቸው ሶስቱም ክፍሎች በተሻለ ይሄኛው በእጥፍ ሰፋት አለው፡፡ ግን ቤት ሳይሆን ኳተት ማጠራቀሚያ ክፍል ነው ማለት ይቻላል፡፡በኤሌክትሮኒክ ዕቃዎች፣በብረታ ብረት ቁርጥራጮች፣በተበላሹ ቴሌቨዢኖች፣ሬዲዬኖች
ገመዳ ገመዶች ተሞልቷል፡፡ዕድሜው ከ1ዐ የማይበልጠው የሰውነቱ ግዙፍነት ግን የ15 ዓመት ታዳጊ የሚያስመስለው ድንቡሽቡሽ ልጁ ኮተቶቹ መሀከል ወለል ላይ ተዘርፍጦ ላፕቶፕ ኮምፒተር ላይ አፍጥጧል፡፡ድምፅ ብታሰማውም ሊሰማት አልቻለም፡፡ሹክክ ብላ ወጥታ ወደ ሳሎን ተመለሰች እና ስላየችው ነገር በግርምት ማሰላሰል ጀመረች፡፡
አንድ ሰዓት ሲሆን ሁሉም የእለት ስራቸውን አጠናቀው ከየአስተማሪዎቻቸው ጋር ከየክፍላቸው ወጡ፤ ከወንድዬው ልጅ በስተቀር፡፡ ሠላምንም አስተማሪዋ ደግፎት አመጣትና ከእሷ ጐን እንድትቀመጥ ከረዳት በኃላ‹‹ይቅርታ ቅድም በስራ መሀል ስለነበርኩ በቅጡ አላናገርኩሽም…የቤቱ ህግ ነው፡፡ ከሁሉ በፊት ስራ ይቀድማል፡፡አላዛር እባላለሁ፡፡››በማለት እጁን ለሰላምታ ዘረጋላት፡፡ እሷም እየጨበጠችው‹‹ሶፊያ እባላለሁ›› አለችው፡፡
‹‹አሁን ሠላምን መጠየቅ ትችያለሽ..ያው ከጎንሽ አስቀምጪልሻለሁ፡፡ እኔ ሽንት ቤት ደርሼ መጣው›› ብሎ ወደ ጓሮ ሄደ ::
‹‹አመሰግናለሁ››ብላው የሰላምን ግንባሯን ሳመቻት፡፡
‹‹ትመጪያለሽ ብዬ ስጠብቅሽ ነበር ::>> አለቻት ሠላም በመምጣቷ መደሰቷን በፈገግታዋ እያረጋገጠችላት፡፡
‹‹ይሄው መጣሁልሽ፤ ለመሆኑ የሚያምሽ ተሻለሽ?»
‹‹አዎ ...ዛሬ ሚጠዘጥዘኝ ትቶኛል፡፡››
‹‹አይ ጥሩ ነው፡፡››ንግግሯን ሳትጨርስ ሌሎቹ ልጆች ከያሉበት መጥተው ወረሯት ፡፡ግማሹ ግንባሯን ግማሹ ጉንጮን ሳሟት፡፡እሷም በየተራ ሳመቻቸው፡፡ለሚያያቸው ዕውቂያቸው የአንድ ቀን ብቻ አይመስልም፡፡
አላዛር ከጓሮ ተመለሰና ከሚጠብቁት ጓደኞቹ ጋር ከተቀላቀለ በኃላ ድምፅን ከፍ አድርጐ << ሶፊ ልንሄድ ነው››ሲላት ልጆቹን ‹‹ቆይ አንዴ መጣሁ >>ብላ ከተቀመጠችበት ተነሳችና ወደ እነ አላዛር ሄደች፡፡
‹‹ይቅርታ እኔ የታዲ ዘመድ ነኝ፤ ከሁላችሁም ጋር ብተዋወቅ ደስ ይለኛል፡፡››
አይነስውሯ ቀድማ ለሰላምታ እጇን እየዘረጋችላት‹‹ፅዬን እባላለሁ›› አለቻት፡፡
‹‹ዶ/ር ሶፍያና፡፡››
‹‹ቤቲ..ቤተልሄም፡፡›› እባላለሁ..ሌላዋ ቀጠለች፡፡
አላዛር መሀል ገብቶ ማብራሪያ በመስጠት ቀጠለ ‹‹...ፂ እንዳየሻት አሪፍ የሙዚቃ ሰው ነች፡፡ጊታር እና ፒያኖ ነፍስ አድርጋ ትጫወታለች፡፡የያሬድ ግርፋ ነች፤ በሞያዋ የሙዚቃ አስተማሪ ነች፡፡እዚህም እንዳየሻት የሄለን እና የሚኪያ የሙዚቃ አስተማሪ ነች፡፡…
ቤቲ ደግሞ ሀይ‐ስኩል አማርኛ ቲቸር ነች፡፡
የስድስት ኪሎ ምሩቅ ነች፡፡እዚህ ያሉትን ህፃናት አማርኛም ሆነ እንግሊዘኛ ቋንቋ በፕሮግራም
ታስተምራቸዋለች፡፡አንዳንዴ
ሂሳብም ቀልቀል ለማድረግ ትሞክራለች ግን ቀሺም ነች፡፡ሂሳብ እና ጠቅላላ ዕውቀትን በተመለከተ ጂኒዬሱ ነው የሚያስተምራቸው፡፡
ጂኒዬሱ ስል ታዲዬስን ማለቴ ነው፡፡እኔ ያው
እዚህ ቤት የቀለም ሽታ የምትወድ አንድ ሰላም
የምትባል ልዩ ነፍስ ያላት ልጅ አለች ፤እሷን ስዕል አስተምራታለሁ፡፡አስተምራታለሁ ማለት
እንኳን ይከብዳል ስትስል
አያታለው፤የምትፈልገውን ቁሳቁስ አቀብላታለው ማለቱ ነው የሚሻለው ፡፡
ምክንያቱም አሁን ባለንበት ሁኔታ ችሎታችን እኩል ነው፤ከስድስት ወር በኃላ ደግሞ እኔ ቁጭ ብዬ ከእሷ መማሬ አይቀርም፡፡››
👍78❤11👎1👏1🤔1
‹‹በጣም ደስ ይላል፡፡እዚህ በትርፍ ጊዜያችሁ እነሱን እየረዳችሁ ነው አይደል?››
‹‹አይ በክፍያ ነው..ከእሁድ በስተቀር ከትምህርት ቤት ሲመለሱ በቀን ለሁለት ሰዓት እናስተምራቸዋለን፡፡የአንድ ሰዓት ይከፈለናል፤የአንዱ ሰዓት ደግሞ የእኛ ምርቃት ነው፡፡››
‹‹ጂኒዬሱ ነዋ..በየወሩ ሁለት ሁለት ሺ ብር ለእያንዳንዳችን ይከፍለናል.፡፡በይ ሌላውን ሌላ ጊዜ …አሁን እንሂድ››
ግራ ገባት ::ይሄ ታዲዬስ የሚባል ልጅ ምን አይነት እንቆቅልሽ የሆነ ሰው ነው?አንድ በሊስትሮና በመፅሀፍ ሽያጭ ሚተዳደር ልጅ እንዴት ይሄንን ሁሉ ወጪ ሸፍኖ እንዲህ አይነት የተለየ ነገር ሊሰራ ይችላል? በውስጧ ጠየቀች፡፡
‹‹ቆይ ወንዱ ልጅ እዛ ቅራቅንቦ ውስጥ ላፕቶፕ እየጎረጐረ ነበር..››
‹‹ሳይንቲስቱን ነው?››አላት ቀልቃላው አላዛር፡፡
‹‹ወፍራሙን ህፃን ልጅ እኮ ነው ምልህ››
‹‹ገብቶኛል..እሺ እሱ ምን?››
‹‹ማለቴ ማንም አስተማሪ አጠገቡ የለም ምን እየሰራ ነው?››
‹‹ጥያቄሽ ሰፊ ነው..በአጭሩ ግን እሱ ምንም ዓይነት አስተማሪ ሊያስተምረው አይችልም፡፡ ከትምህርት ቤት መጨረሻ ደረጃ ነው የሚወጣው ፡፡ ሰነፍ ስለሆነ አይምሰልሽ ዕውቀቱ ከአስተማሪዎቹ ችሎታ በላይ ስለሆነ አይረዱትም፤እሱም እነሱን መረዳት ይቸግረዋል፡፡ እንደምታውቂው የእኛ ሀገር ትምህርት ከወረቀት ወደአዕምሮ ኮፒ ማድረግ ከዛ በፈተና ቀን ከአዕምሮ ደግሞ ወደ ወረቀት መልሶ ኮፒ ማደረግ ወሃ ቅዳ ውሃ መልስ አይነት ነው፡፡ሳይንቲስቱ ግን እንደዛ አይነት ነገር አይገባውም፡፡ እሱ የሚግባባው ከታዲዬስ ጋር ብቻ ነው፡፡የፈጠራ ችሎታውን ግን አትጠይቂኝ..፡፡ወደፊት ኢትዬጵያ ሚያልፍላት ከሆነ በዚህ ልጅ ይመስለኛል
፤ቶማስ ኤዲሰን በይው..፡፡ በይ ብዙ ጥያቄ ያለሽ ትመስያለሽ..ለሌላ ጊዜ አቆይው፡፡››
ሁሉም ተሰናብተዋት ሲወጡ ከኃላ እየተጐተተ ለነበረው አላዛር የቢዝነስ ካርዷን አቀበለችው ‹‹ደውልልኝ››ደስ እያለው ወጣ፡፡
እነሱን ሸኝታ የሳሎኑን በራፍ ዘጋችና ወደ ልጆቹ
ተመለሰች... እየተገረመች፡፡እዚህ ቤት አንድ ድምጻዊ ለመሆን ተስፋው ያላት ልጅ ፤አንድ የሙዚቃ ተጫዋች ለመሆን በሚንተከተክ
ፍላጎት የተሞላች ልጅ፤አንድ የወደፊት ሰዓሊ ለመሆን መንገዱን የጨበጠች ልጅ ..አንድ በልጅነቱ በፈጠራ ጥማት ተለከፈ
ልጅ‹‹..ይገርማል !!››አለች፡፡ እኚ ሁሉ ባለ ትልቅ
ርዕይ ባለቤት ህጻናት የተገኙት ከየጎዳናው
ነው፡፡ይሄ ማለት ደግሞ ስንቱ ሰብሳቢና መንገድ መሪ አጥቶ በየቆሻሻ ጉድጓዱ የአንጀቱን የረሀብ ጩኸት ለማስታገስ ሲል
የተጣለ ምግብ በመፈለግ ብቻ ተሰነካክሎና ባክኖ ቀርቶ ይሆን? እግዜር ብቻ ነው የሚያውቀው ፡፡
‹‹እሺ ልጆች አሁን ስጦታ አምጥቼላችኃለው..ግን በመጀመሪያ ወንድማችሁን ጥሩት››አለች፡፡
‹‹አይ እሱ እኮ አይጠራም፡፡እራሱ ሲፈልግ ነው የሚወጣው፡፡››ሀሊማ ነች የመለሰችው፡፡
<<ለምን?>>
‹‹አይሰማማ፡፡ቢሰማም እሺ አይልም፡፡››አለቻት ሰላም፡፡
... ፔሳታሎቹ ወስጥ የታጨቁትን ቁሳቁች ሰፊው ጠረጴዛው ላይ ተራ በተራ ዘረገፈችው፡፡ ልብሶች፣ኳሶች፣ደብተር፣እስኪሪብቶዎች፣መፅሀፎች ያላመጣችላቸው ነገር የለም፡፡
ለእያንዳንዱ ሚደርሳቸውን ያህል ለየብቻ አምስት ቦታ መደበችና የየራሳቸውን በየተራ አስረከበቻቸው ፤በቦታው ያልተገኘውን የሙሴን ብቻ አስቀርታ፡፡
ስጦታውን ተከትሎ ከልጆቹ ፈገግታና ፍንጠዝያ ጠብቃ ነበር፡፡ልጆቹ ግን መፅሀፉን
ብቻ አስቀርተው ሌሎች ስጦታዎቹን ተራ በተራ መለሱላት፡፡
‹‹ምነው...አልወዳዳችሁትም እንዴ?›› ‹‹በጣም ወደነዋል እናመሰግናለን፡፡ግን ከመጽሀፉ ውጭ ልንቀበልሽ አንችልም፡፡›› ሄለን ነች የመለሰችላት፡፡
<< ለአሁኑ ሚበቃንን ያህል ስላለን ነው፡፡ወደ ፊት የሚያስፈልገን ከሆነ ደግሞ ታዲን ማስገዛት እንችላለን፡፡ሰውን ማስቸገር አግባብ አይደለም፡፡››
‹‹እኔ መቼ አስቸገራችሁኝ አልኩ?››
‹‹አንቺ ባትይም አይገባም፡፡በሰው ስጦታ ላይ ጥገኛ መሆን ለእኛ ይከብዳል፡፡ ከቤተሰቦቻችን የተለየ ህይወት መኖር ነው ምንፈልገው፡፡››አለች ሰላም፡፡
ዶክተር ሶፊያ ግራ ገባት ፤ ‹‹የቱን ከየቱ አገናኝተው ነው ያቆላለፉት?›› ስትል አሰበች፡፡ ምን ማለት እንዳለባት ግራ ገብቷት እያሰላሰለች ሳለ ታዲዬስ ገብቶ ተቀላቀላቸው፡፡ ለሁሉም ሰላምታውን ካደረሰ በኃላ‹‹ምን ሆናችሁ?››ሲል ጠየቃቸው፡፡
‹‹እኔ እንጃ እነዚህን ስጦታዎች ልጆችህን ያስደስታሉ ብዬ ገዝቼ አመጣሁ፤ግን ከመጽሀፉ በስተቀር አንቀበልም አሉኝ››
‹‹እስቲ ዶክተር ቁጭ በይና እንነጋገርበት፤ እናንተም ተቀመጡ፡፡›› ብሎ ቀድሞ ወንበር ያዘ፡፡ ሁሉም ትዕዛዙን አክብረው ተቀመጡ ፡፡ መናገር ጀመረ፡፡
‹‹እንግዲህ ይህቺ እንግዳችንን በእኛ ቅር እንደተሰኘች ነው የምትናገረው፡፡ስጦታ አምጥታላችሁ ነበር እናንተ ግን ልትቀበሏት አልቻላችሁም ለምን ?
‹‹አንቀበልም አላልንም...አመሰግነን ያመጣችውን መጽሀፍ ወስደናል›› ሄለን ነች የመለሰችው፡፡
‹‹ልብሶቹን፤መጫወቻዎቹን ሌሎች ሁሉንም ያመጣሁላችሁን ግን እምቢ ብላችኋል››
‹‹አዎ መልሰናል››ሰላም መለሰች..፡፡
ታዲዬስ ቀጠለ ‹‹ምክንያታችሁን ለእኔም ለእሷም አስረዱን እስቲ ሚጣ ቀጥይ፡፡ ለምንድነው ስጦታውን አልቀበልም ያልሽው?››
‹‹ለምሳሌ ያመጣችልኝ ቀሚስንና ቢጃማን አልቀበልም ያልኩት የሚበቃኝን ያህል ስላለኝ ነው?>>
‹‹የሚበቃኝን ያህል ማለት ምን ማለት ነው?››ዶ/ር ሶፊያ በገረሜታ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ሦስት ቀሚስ እና ሁለት የለሊት ቢጃማ
‹‹ታዲያ ተጨማሪ ሌላ ቢኖርሽ ምን ችግር አለው?»
‹‹ችግር አለው እንጂ፡፡ብዙ ልጆች አንድ ልብስ እንኳን አጥተው እራቁታቸውን እየሄዱ እንደሆነ እያወቅኩ እኔ ደግሞ የማለብሰውን ብዙ ልብስ መሰብሰብ እንዴት ይሆንልኛል?››
ሶፊያ ግራ ገባት ፡፡አንድ የዘጠኝ አመት ልጅ እንዴት እንዲህ ልታስብ ትችላለች፡፡መልስ ባታገኝም እራሷን ጠየቀች፡፡
‹‹እሺ ሄለንስ ምክንያትሽን ልትገልጪልን ትችያለሽ?ምክንያትሽ ከሰላም ጋር ተመሳሳይ ነው?>>
‹‹አዎ ሰላም ያለችው እንዳለ ሆኖ በተጨማሪ ምናገረው ለምሳሌ አንተ ያሉህ ልብሶች ሶስት ሱሪዎች እና ሶስት ሸሚዞች እና ሶስት ጫማዎች ናቸው፡፡በቁም ሳጥን ሙሉ የሚሞላ ልብስ ገዝተህ ዝንጥ ማለት ትችል ነበር፡፡ግን አንተ በቂዬ ነው ብለህ ለዛ የምታወጣውን ብር ለእኛም ሆነ ለሌሎች ልብስ እየገዛህ ታለብስበታህ፡፡የእኔ ምሳሌ አንተ ነህ::አሁን የሚያስፈልገኝን ያህል ልብስ አለኝ... ከዛ በላይ መሰብሰብ ስግብግብነት ነው::››
መልሱ ምን እንደሚሆን እያወቀ ጠየቃቸው <<የሁላችሁም መልስ ተመሳሳይ ነው? >> ተመሳሳይ መሆኑን ሁሉም ግንባራቸውን በመነቅነቅ አረጋገጡለት፡፡
ዶ/ር ልጆቼ ያሉትን ሰምተሸል…የምትይው ይኖርሻል?››
ለተወሰነ ሰከንድ ዝም አለችና ‹‹ምን እንደምል አላውቅም::ትናንት ባጋጣሚ ሳያችሁ በጣም ስለወደድኳችሁ ነው የፍቅሬን መጠን ይገልፅልኛል በሚል ተስፋ ካለኝ ገንዘብ ላይ በጣም ጥቂቷን ቆንጥሬ እነዚህን ስጦታዎች ገዝቼላችሁ የመጣሁት፡፡ያንን በማድረጌ እኔ የተደሰትኩትን ያህል እናንተም በደስታ ትቀበሉኛላችሁ ብዬ በማሰብ ነበር፡፡አሁን ለምሳሌ እኔ በቤቴ ያለኝ ልብስ ቁም ሳጥን ሙሉ ሞልቶ ሌሎች ትላልቅ ሻንጣዎች ተጠቅጥቆ ተርፏል፡፡ምን አልባት በቁጥር 5ዐዐ በላይ እንደሚሆን እገምታለሁ፡፡ ነገር ግን አሁን ያንተ ልጆች እንደተናገሩት ትርፍ ልብሶች
እንዳሉኝ ተሰምቶኝ አያውቅም
‹‹አይ በክፍያ ነው..ከእሁድ በስተቀር ከትምህርት ቤት ሲመለሱ በቀን ለሁለት ሰዓት እናስተምራቸዋለን፡፡የአንድ ሰዓት ይከፈለናል፤የአንዱ ሰዓት ደግሞ የእኛ ምርቃት ነው፡፡››
‹‹ጂኒዬሱ ነዋ..በየወሩ ሁለት ሁለት ሺ ብር ለእያንዳንዳችን ይከፍለናል.፡፡በይ ሌላውን ሌላ ጊዜ …አሁን እንሂድ››
ግራ ገባት ::ይሄ ታዲዬስ የሚባል ልጅ ምን አይነት እንቆቅልሽ የሆነ ሰው ነው?አንድ በሊስትሮና በመፅሀፍ ሽያጭ ሚተዳደር ልጅ እንዴት ይሄንን ሁሉ ወጪ ሸፍኖ እንዲህ አይነት የተለየ ነገር ሊሰራ ይችላል? በውስጧ ጠየቀች፡፡
‹‹ቆይ ወንዱ ልጅ እዛ ቅራቅንቦ ውስጥ ላፕቶፕ እየጎረጐረ ነበር..››
‹‹ሳይንቲስቱን ነው?››አላት ቀልቃላው አላዛር፡፡
‹‹ወፍራሙን ህፃን ልጅ እኮ ነው ምልህ››
‹‹ገብቶኛል..እሺ እሱ ምን?››
‹‹ማለቴ ማንም አስተማሪ አጠገቡ የለም ምን እየሰራ ነው?››
‹‹ጥያቄሽ ሰፊ ነው..በአጭሩ ግን እሱ ምንም ዓይነት አስተማሪ ሊያስተምረው አይችልም፡፡ ከትምህርት ቤት መጨረሻ ደረጃ ነው የሚወጣው ፡፡ ሰነፍ ስለሆነ አይምሰልሽ ዕውቀቱ ከአስተማሪዎቹ ችሎታ በላይ ስለሆነ አይረዱትም፤እሱም እነሱን መረዳት ይቸግረዋል፡፡ እንደምታውቂው የእኛ ሀገር ትምህርት ከወረቀት ወደአዕምሮ ኮፒ ማድረግ ከዛ በፈተና ቀን ከአዕምሮ ደግሞ ወደ ወረቀት መልሶ ኮፒ ማደረግ ወሃ ቅዳ ውሃ መልስ አይነት ነው፡፡ሳይንቲስቱ ግን እንደዛ አይነት ነገር አይገባውም፡፡ እሱ የሚግባባው ከታዲዬስ ጋር ብቻ ነው፡፡የፈጠራ ችሎታውን ግን አትጠይቂኝ..፡፡ወደፊት ኢትዬጵያ ሚያልፍላት ከሆነ በዚህ ልጅ ይመስለኛል
፤ቶማስ ኤዲሰን በይው..፡፡ በይ ብዙ ጥያቄ ያለሽ ትመስያለሽ..ለሌላ ጊዜ አቆይው፡፡››
ሁሉም ተሰናብተዋት ሲወጡ ከኃላ እየተጐተተ ለነበረው አላዛር የቢዝነስ ካርዷን አቀበለችው ‹‹ደውልልኝ››ደስ እያለው ወጣ፡፡
እነሱን ሸኝታ የሳሎኑን በራፍ ዘጋችና ወደ ልጆቹ
ተመለሰች... እየተገረመች፡፡እዚህ ቤት አንድ ድምጻዊ ለመሆን ተስፋው ያላት ልጅ ፤አንድ የሙዚቃ ተጫዋች ለመሆን በሚንተከተክ
ፍላጎት የተሞላች ልጅ፤አንድ የወደፊት ሰዓሊ ለመሆን መንገዱን የጨበጠች ልጅ ..አንድ በልጅነቱ በፈጠራ ጥማት ተለከፈ
ልጅ‹‹..ይገርማል !!››አለች፡፡ እኚ ሁሉ ባለ ትልቅ
ርዕይ ባለቤት ህጻናት የተገኙት ከየጎዳናው
ነው፡፡ይሄ ማለት ደግሞ ስንቱ ሰብሳቢና መንገድ መሪ አጥቶ በየቆሻሻ ጉድጓዱ የአንጀቱን የረሀብ ጩኸት ለማስታገስ ሲል
የተጣለ ምግብ በመፈለግ ብቻ ተሰነካክሎና ባክኖ ቀርቶ ይሆን? እግዜር ብቻ ነው የሚያውቀው ፡፡
‹‹እሺ ልጆች አሁን ስጦታ አምጥቼላችኃለው..ግን በመጀመሪያ ወንድማችሁን ጥሩት››አለች፡፡
‹‹አይ እሱ እኮ አይጠራም፡፡እራሱ ሲፈልግ ነው የሚወጣው፡፡››ሀሊማ ነች የመለሰችው፡፡
<<ለምን?>>
‹‹አይሰማማ፡፡ቢሰማም እሺ አይልም፡፡››አለቻት ሰላም፡፡
... ፔሳታሎቹ ወስጥ የታጨቁትን ቁሳቁች ሰፊው ጠረጴዛው ላይ ተራ በተራ ዘረገፈችው፡፡ ልብሶች፣ኳሶች፣ደብተር፣እስኪሪብቶዎች፣መፅሀፎች ያላመጣችላቸው ነገር የለም፡፡
ለእያንዳንዱ ሚደርሳቸውን ያህል ለየብቻ አምስት ቦታ መደበችና የየራሳቸውን በየተራ አስረከበቻቸው ፤በቦታው ያልተገኘውን የሙሴን ብቻ አስቀርታ፡፡
ስጦታውን ተከትሎ ከልጆቹ ፈገግታና ፍንጠዝያ ጠብቃ ነበር፡፡ልጆቹ ግን መፅሀፉን
ብቻ አስቀርተው ሌሎች ስጦታዎቹን ተራ በተራ መለሱላት፡፡
‹‹ምነው...አልወዳዳችሁትም እንዴ?›› ‹‹በጣም ወደነዋል እናመሰግናለን፡፡ግን ከመጽሀፉ ውጭ ልንቀበልሽ አንችልም፡፡›› ሄለን ነች የመለሰችላት፡፡
<< ለአሁኑ ሚበቃንን ያህል ስላለን ነው፡፡ወደ ፊት የሚያስፈልገን ከሆነ ደግሞ ታዲን ማስገዛት እንችላለን፡፡ሰውን ማስቸገር አግባብ አይደለም፡፡››
‹‹እኔ መቼ አስቸገራችሁኝ አልኩ?››
‹‹አንቺ ባትይም አይገባም፡፡በሰው ስጦታ ላይ ጥገኛ መሆን ለእኛ ይከብዳል፡፡ ከቤተሰቦቻችን የተለየ ህይወት መኖር ነው ምንፈልገው፡፡››አለች ሰላም፡፡
ዶክተር ሶፊያ ግራ ገባት ፤ ‹‹የቱን ከየቱ አገናኝተው ነው ያቆላለፉት?›› ስትል አሰበች፡፡ ምን ማለት እንዳለባት ግራ ገብቷት እያሰላሰለች ሳለ ታዲዬስ ገብቶ ተቀላቀላቸው፡፡ ለሁሉም ሰላምታውን ካደረሰ በኃላ‹‹ምን ሆናችሁ?››ሲል ጠየቃቸው፡፡
‹‹እኔ እንጃ እነዚህን ስጦታዎች ልጆችህን ያስደስታሉ ብዬ ገዝቼ አመጣሁ፤ግን ከመጽሀፉ በስተቀር አንቀበልም አሉኝ››
‹‹እስቲ ዶክተር ቁጭ በይና እንነጋገርበት፤ እናንተም ተቀመጡ፡፡›› ብሎ ቀድሞ ወንበር ያዘ፡፡ ሁሉም ትዕዛዙን አክብረው ተቀመጡ ፡፡ መናገር ጀመረ፡፡
‹‹እንግዲህ ይህቺ እንግዳችንን በእኛ ቅር እንደተሰኘች ነው የምትናገረው፡፡ስጦታ አምጥታላችሁ ነበር እናንተ ግን ልትቀበሏት አልቻላችሁም ለምን ?
‹‹አንቀበልም አላልንም...አመሰግነን ያመጣችውን መጽሀፍ ወስደናል›› ሄለን ነች የመለሰችው፡፡
‹‹ልብሶቹን፤መጫወቻዎቹን ሌሎች ሁሉንም ያመጣሁላችሁን ግን እምቢ ብላችኋል››
‹‹አዎ መልሰናል››ሰላም መለሰች..፡፡
ታዲዬስ ቀጠለ ‹‹ምክንያታችሁን ለእኔም ለእሷም አስረዱን እስቲ ሚጣ ቀጥይ፡፡ ለምንድነው ስጦታውን አልቀበልም ያልሽው?››
‹‹ለምሳሌ ያመጣችልኝ ቀሚስንና ቢጃማን አልቀበልም ያልኩት የሚበቃኝን ያህል ስላለኝ ነው?>>
‹‹የሚበቃኝን ያህል ማለት ምን ማለት ነው?››ዶ/ር ሶፊያ በገረሜታ ጠየቀቻት፡፡
‹‹ሦስት ቀሚስ እና ሁለት የለሊት ቢጃማ
‹‹ታዲያ ተጨማሪ ሌላ ቢኖርሽ ምን ችግር አለው?»
‹‹ችግር አለው እንጂ፡፡ብዙ ልጆች አንድ ልብስ እንኳን አጥተው እራቁታቸውን እየሄዱ እንደሆነ እያወቅኩ እኔ ደግሞ የማለብሰውን ብዙ ልብስ መሰብሰብ እንዴት ይሆንልኛል?››
ሶፊያ ግራ ገባት ፡፡አንድ የዘጠኝ አመት ልጅ እንዴት እንዲህ ልታስብ ትችላለች፡፡መልስ ባታገኝም እራሷን ጠየቀች፡፡
‹‹እሺ ሄለንስ ምክንያትሽን ልትገልጪልን ትችያለሽ?ምክንያትሽ ከሰላም ጋር ተመሳሳይ ነው?>>
‹‹አዎ ሰላም ያለችው እንዳለ ሆኖ በተጨማሪ ምናገረው ለምሳሌ አንተ ያሉህ ልብሶች ሶስት ሱሪዎች እና ሶስት ሸሚዞች እና ሶስት ጫማዎች ናቸው፡፡በቁም ሳጥን ሙሉ የሚሞላ ልብስ ገዝተህ ዝንጥ ማለት ትችል ነበር፡፡ግን አንተ በቂዬ ነው ብለህ ለዛ የምታወጣውን ብር ለእኛም ሆነ ለሌሎች ልብስ እየገዛህ ታለብስበታህ፡፡የእኔ ምሳሌ አንተ ነህ::አሁን የሚያስፈልገኝን ያህል ልብስ አለኝ... ከዛ በላይ መሰብሰብ ስግብግብነት ነው::››
መልሱ ምን እንደሚሆን እያወቀ ጠየቃቸው <<የሁላችሁም መልስ ተመሳሳይ ነው? >> ተመሳሳይ መሆኑን ሁሉም ግንባራቸውን በመነቅነቅ አረጋገጡለት፡፡
ዶ/ር ልጆቼ ያሉትን ሰምተሸል…የምትይው ይኖርሻል?››
ለተወሰነ ሰከንድ ዝም አለችና ‹‹ምን እንደምል አላውቅም::ትናንት ባጋጣሚ ሳያችሁ በጣም ስለወደድኳችሁ ነው የፍቅሬን መጠን ይገልፅልኛል በሚል ተስፋ ካለኝ ገንዘብ ላይ በጣም ጥቂቷን ቆንጥሬ እነዚህን ስጦታዎች ገዝቼላችሁ የመጣሁት፡፡ያንን በማድረጌ እኔ የተደሰትኩትን ያህል እናንተም በደስታ ትቀበሉኛላችሁ ብዬ በማሰብ ነበር፡፡አሁን ለምሳሌ እኔ በቤቴ ያለኝ ልብስ ቁም ሳጥን ሙሉ ሞልቶ ሌሎች ትላልቅ ሻንጣዎች ተጠቅጥቆ ተርፏል፡፡ምን አልባት በቁጥር 5ዐዐ በላይ እንደሚሆን እገምታለሁ፡፡ ነገር ግን አሁን ያንተ ልጆች እንደተናገሩት ትርፍ ልብሶች
እንዳሉኝ ተሰምቶኝ አያውቅም
👍89❤4
ትናንት እራሱ ለእነሱ ይሄንን ስጦታ ስገዛ እግረ መንገዴን ለራሴም ሶስት ጥንድ ጫማዎች ገዝቼያለሁ.. እቤቴ ግን ቢያንስ ከመቶ በላይ ጫማዎች አሉኝ ፡፡በእነሱ ግን መርካት ባለመቻሌ እና ተጨማሪ ያስፈልገኛል ብዬ በማመኔ ነው የገዛሁት፤እንጂ ትርፍ ይሆናል ብዬ አላሰብኩም፡፡አነዚህ አንድ ፍሬ ህፃናት ግን ከምንጠቀምበት በላይ አንሰበስብም ሲሉ እነሱን ተከራክሬ ለማሳመን ምን አይነት ሞራል ይኖረኛል?›› ብላ ንግግሯን ደመደመች፡፡
‹‹በቃ እኔ ላስታርቃችሁ ፤ አሁን እሷ ቅር እንዳይላት ያመጣችውን ስጦታ አመስግናችሁ ተቀበሏት፡፡ከዛ እሁድ ጓደኞቻችንን ልንጠይቃቸው ስንሔድ ለሚያስፈልጋቸው በእሷ ስም እንሰጣቸዋለን..ይሄ ያስማማናል?፡፡››
ሁሉም በፈገግታ ሀሳቡን ተቀበሉት፡፡የእሷን ጉንጭ በማመስገን እየሳሙ መልሰውላት የነበረውን ስጦታ ከያስቀመጡበት በመውሰድ ወደመቀመጫችው ተመለሱ፡፡
በዚህ ጊዜ ሳይንቲስቱ ሙሴ ከመሸገበት ክፍል ፈንደድ ፈንደድ እያለ መጥቶ ተቀላቀላቸው፡፡ታዲዬስ ወደራሱ ስቦ ግንባሩን ሳመው፡፡ዶክተር ሶፊያ የሙሴ ድርሻ የሆነውን ስጦታ ልትሰጠው ስትንቀሳቀስ‹‹ዶ/ር ተይው ….እሱን አስረድቶ ለማሳመን ለሊቱም አይበቃንም፡፡ይልቅ አሁን ሁላችንም ለእራት እንውጣ >> የሚል ሀሳብ አቀረበ፡፡›› ሁሉም በደስታ ተስማሙ፡፡
‹‹እስክትዘገጃጁ ታክሲ ጋር ልደውል?››
‹‹እኔ መኪና ይዤያለሁ›› አለችው ዶክተሯ፡፡
‹‹ውጭ የቆመችው መኪና ያንቺ ነች እንዴ?››
<<አዎ>>
ተያይዘው ወጡ፡፡መኪናው ውስጥ ገቡ፡፡ ውጪው በጣም ጨልሟል፡፡ ከተማዋ መብራት ሙሉ በሙሉ ጠፍቷል፡፡
‹‹መብራት ጠፍቷል እንዴ..?እናንተ ጋር ጄኔሬተር አለ ማለት ነው ? >> ስትል ጠየቀችው ዶክተር ሶፊያ እነሱ ቤት ለብቻው ተነጥሎ መብራት እየበራበት ሞሆኑ ገርሟት፡፡
‹‹እኛ እኮ ሀገሪቱን በመብራት አናስቸግርም ..እድሜ ለሙሴ እራሳችንን ችለናል፡፡››
<<እንዴት?>>
‹‹ሙሴ በራሱ ፈጠራ ከፀሀይ ሃይል የሚያመነጭ የራሳችንን በቂ ሀይል እንድናገኝ አድርጎናል..ነጻ ከወጣን አንድ አመት ሆነን፡፡ መብራት ኃይል የራሱን ቆጣሪ በብስጭት መሰለኝ ከቆረጠው ቆየ፡፡››
ወደ ግዙፉ ታዳጊ በአትኩሮት እየተመለከተች‹‹ይሄ ሙሴ ነው የሰራው ?>> ስትል ባለማመን ደግማ ጠየቀችው ፡፡
‹‹አዎ ይሄ የእኛ ሙሴ፡፡›› ፍርጥም ብሎ አረጋገጠላት
‹‹ለመሆኑ ስንት አመቱ ነው?››
‹‹አስር ወይም አስራ አንድ ይሆነዋል..ነገሮችን ለመስራት ግን ዋናው ዕድሜ አይመስለኝም ስጦታ እና ጥረት ካለ የእናት ጡት መጥባት ሳያቆሙ በፊትም ተዓምር መስራት ይቻላል፡፡››አለት፡፡
‹‹እሱስ እውነትህን ነው... በእንደ እናንተ አይነት የጉድ ቤት የማይቻል ነገር የለም !! እሺ አሁን ወዴት ልንዳ?›› አለችው፡፡
በከተማዋ የሚገኙ የትልቅ ሆቴል ስም ነገራት፤ ወደዛው አሽከረከረች፡፡‹‹እዛ አካባቢ የሚገኝ ምግብ ቤት ለመጠቀም ፈልጎ ይሆናል፡፡›› ስትል ገመተች፡፡ደረሱ ፡፡መኪናውን ቦታ አሲይዛ አቆመች፡፡
ወርደው ግን ያመሩት እንደጠበቀችው ወደአነስተኛ ምግብ ቤት ሳይሆን ወደ ዋናው ባለኮከብ ሆቴል ነው፡፡ትናንት እራት ከበሉበት የአሮጊቷ ምግብ ቤት ጋር ሲነፃፀር የሲኦል እና የገነት አይነት ልዩነት አለው፡፡ተከትላቸው ወደሆቴሉ ገባች፡፡ሲገቡ አስተናጋጆቹ ሁሉ ተንጋግተው በመምጣት በሞቀ ሰላምታና በደመቀ ፈገግታ ተቀብለው ቦታ ሰጧቸው፡፡ እያንዳንዶቹን ህፃናት በየስማቸው እየጠሯቸው ያናግሯቸው ነበር፡፡ሶፊያ በጣም ነበር የተደመመችው፡፡የቤቱ ቋሚ ደንበኞች እንደሆኑ በእርግጠኝነት አመነች፡፡ለአንድ ሰዓት ያህል እየተጫወቱና እየተዝናኑ ከቆዩ በኃላ መልሳ ቤት ድረስ ሸኘቻቸው፡፡ሲለያዩ‹‹ለእራት ግብዣው አመሰግናለሁ፡፡››አለችው፡፡
<<ችግር የለውም›› መለሰላት ታዲዬስ፡፡
‹‹አንድ ነገር ላስቸግርህ?››
<<ምን ልታዘዝ>>
‹‹ነገ ቁርስ ብጋብዝህ ደስ ይለኛል?››
<< ነገ?>>
‹‹አዎ ነገ ሁለት ሰዓት አካባቢ፡፡››
‹‹ይቻላል ስራ ቦታ ታገኚኛለሽ፡፡››አላትና ልጆቹን ይዞ ወደ ቤቱ ሲገባ እሷም መኪና• አስነስታ በተደመመ ስሜት ወደ ቤርጎዋ ተመለሰች፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች የዩቲዩብ ቻናሉን #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ እንጂ ለ500 እኮ ትንሽ ነው የቀረው እባካቹ ቤተሰቦች
ሰብስክረይብ እያረጋቹ ያደረጋችሁ ደግሞ ሌሎች እዲያደርጉ #Share እያደረጋቹ አመሰግናለሁ፡፡
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
‹‹በቃ እኔ ላስታርቃችሁ ፤ አሁን እሷ ቅር እንዳይላት ያመጣችውን ስጦታ አመስግናችሁ ተቀበሏት፡፡ከዛ እሁድ ጓደኞቻችንን ልንጠይቃቸው ስንሔድ ለሚያስፈልጋቸው በእሷ ስም እንሰጣቸዋለን..ይሄ ያስማማናል?፡፡››
ሁሉም በፈገግታ ሀሳቡን ተቀበሉት፡፡የእሷን ጉንጭ በማመስገን እየሳሙ መልሰውላት የነበረውን ስጦታ ከያስቀመጡበት በመውሰድ ወደመቀመጫችው ተመለሱ፡፡
በዚህ ጊዜ ሳይንቲስቱ ሙሴ ከመሸገበት ክፍል ፈንደድ ፈንደድ እያለ መጥቶ ተቀላቀላቸው፡፡ታዲዬስ ወደራሱ ስቦ ግንባሩን ሳመው፡፡ዶክተር ሶፊያ የሙሴ ድርሻ የሆነውን ስጦታ ልትሰጠው ስትንቀሳቀስ‹‹ዶ/ር ተይው ….እሱን አስረድቶ ለማሳመን ለሊቱም አይበቃንም፡፡ይልቅ አሁን ሁላችንም ለእራት እንውጣ >> የሚል ሀሳብ አቀረበ፡፡›› ሁሉም በደስታ ተስማሙ፡፡
‹‹እስክትዘገጃጁ ታክሲ ጋር ልደውል?››
‹‹እኔ መኪና ይዤያለሁ›› አለችው ዶክተሯ፡፡
‹‹ውጭ የቆመችው መኪና ያንቺ ነች እንዴ?››
<<አዎ>>
ተያይዘው ወጡ፡፡መኪናው ውስጥ ገቡ፡፡ ውጪው በጣም ጨልሟል፡፡ ከተማዋ መብራት ሙሉ በሙሉ ጠፍቷል፡፡
‹‹መብራት ጠፍቷል እንዴ..?እናንተ ጋር ጄኔሬተር አለ ማለት ነው ? >> ስትል ጠየቀችው ዶክተር ሶፊያ እነሱ ቤት ለብቻው ተነጥሎ መብራት እየበራበት ሞሆኑ ገርሟት፡፡
‹‹እኛ እኮ ሀገሪቱን በመብራት አናስቸግርም ..እድሜ ለሙሴ እራሳችንን ችለናል፡፡››
<<እንዴት?>>
‹‹ሙሴ በራሱ ፈጠራ ከፀሀይ ሃይል የሚያመነጭ የራሳችንን በቂ ሀይል እንድናገኝ አድርጎናል..ነጻ ከወጣን አንድ አመት ሆነን፡፡ መብራት ኃይል የራሱን ቆጣሪ በብስጭት መሰለኝ ከቆረጠው ቆየ፡፡››
ወደ ግዙፉ ታዳጊ በአትኩሮት እየተመለከተች‹‹ይሄ ሙሴ ነው የሰራው ?>> ስትል ባለማመን ደግማ ጠየቀችው ፡፡
‹‹አዎ ይሄ የእኛ ሙሴ፡፡›› ፍርጥም ብሎ አረጋገጠላት
‹‹ለመሆኑ ስንት አመቱ ነው?››
‹‹አስር ወይም አስራ አንድ ይሆነዋል..ነገሮችን ለመስራት ግን ዋናው ዕድሜ አይመስለኝም ስጦታ እና ጥረት ካለ የእናት ጡት መጥባት ሳያቆሙ በፊትም ተዓምር መስራት ይቻላል፡፡››አለት፡፡
‹‹እሱስ እውነትህን ነው... በእንደ እናንተ አይነት የጉድ ቤት የማይቻል ነገር የለም !! እሺ አሁን ወዴት ልንዳ?›› አለችው፡፡
በከተማዋ የሚገኙ የትልቅ ሆቴል ስም ነገራት፤ ወደዛው አሽከረከረች፡፡‹‹እዛ አካባቢ የሚገኝ ምግብ ቤት ለመጠቀም ፈልጎ ይሆናል፡፡›› ስትል ገመተች፡፡ደረሱ ፡፡መኪናውን ቦታ አሲይዛ አቆመች፡፡
ወርደው ግን ያመሩት እንደጠበቀችው ወደአነስተኛ ምግብ ቤት ሳይሆን ወደ ዋናው ባለኮከብ ሆቴል ነው፡፡ትናንት እራት ከበሉበት የአሮጊቷ ምግብ ቤት ጋር ሲነፃፀር የሲኦል እና የገነት አይነት ልዩነት አለው፡፡ተከትላቸው ወደሆቴሉ ገባች፡፡ሲገቡ አስተናጋጆቹ ሁሉ ተንጋግተው በመምጣት በሞቀ ሰላምታና በደመቀ ፈገግታ ተቀብለው ቦታ ሰጧቸው፡፡ እያንዳንዶቹን ህፃናት በየስማቸው እየጠሯቸው ያናግሯቸው ነበር፡፡ሶፊያ በጣም ነበር የተደመመችው፡፡የቤቱ ቋሚ ደንበኞች እንደሆኑ በእርግጠኝነት አመነች፡፡ለአንድ ሰዓት ያህል እየተጫወቱና እየተዝናኑ ከቆዩ በኃላ መልሳ ቤት ድረስ ሸኘቻቸው፡፡ሲለያዩ‹‹ለእራት ግብዣው አመሰግናለሁ፡፡››አለችው፡፡
<<ችግር የለውም›› መለሰላት ታዲዬስ፡፡
‹‹አንድ ነገር ላስቸግርህ?››
<<ምን ልታዘዝ>>
‹‹ነገ ቁርስ ብጋብዝህ ደስ ይለኛል?››
<< ነገ?>>
‹‹አዎ ነገ ሁለት ሰዓት አካባቢ፡፡››
‹‹ይቻላል ስራ ቦታ ታገኚኛለሽ፡፡››አላትና ልጆቹን ይዞ ወደ ቤቱ ሲገባ እሷም መኪና• አስነስታ በተደመመ ስሜት ወደ ቤርጎዋ ተመለሰች፡፡
✨ይቀጥላል✨
ቤተሰቦች የዩቲዩብ ቻናሉን #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ እንጂ ለ500 እኮ ትንሽ ነው የቀረው እባካቹ ቤተሰቦች
ሰብስክረይብ እያረጋቹ ያደረጋችሁ ደግሞ ሌሎች እዲያደርጉ #Share እያደረጋቹ አመሰግናለሁ፡፡
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍68🥰4❤3😁2👏1
#ፍቅር_የመሸባት_ሀገር
እዛ ሰው ይሞታል፣ እዛ ደም ይፈሳል
እዚህ ይጨፈራል ፣ እዚህ ይደነሳል
እዛ ሰው ያለቅሳል፣እዚህ ሳቅ ይነግሳል።
፨፨፨
እዛም እኛዎች ነን፣አዚም እኛ ባዮች
የደላን እኛው ነን ፣ እኛው ተበዳዮች
አንድነትን ሰብከን፣የምንሆን ብዙዎች፡፡
እኛው ነን የሞትነው፣እኛው ነን ቀባሪ
እኛው ነን ሙሾ አውራጅ፣እኛው ነን ጨፋሪ
አንድ ነን እያልን ፣ ልዩነት ፈጣሪ፡፡
፨፨
እዛ እኛ ስንሞት፣ እዚ እኛ ስንጨፍር
እዛ እኛን ስንቀንስ፣እዚ እኛን ስንደምር
ሙሾን ከደስታ ጋር የምንደባልቀው
እኛው እያነባን ፣ እኛው የምንስቀው
እኛው ለነፃነት ፣ ታግለን የምናልቀው
እኛው ባርነትን፣ፈቅደን የምንሞቀው
እዚ እየረሳን ፣ እዛ ም'ናፍቀው
ፍቅር መሽቶብን ነው፡፡
፨፨
እንዲህ ነው ሚኖረው....
ፍቅር የመሸበት፣ሀቅ ያልገባው ሀገር
እዛ እኛ ሙሾ አውራጅ ፣ እኛ አዚ ምንጨፍር፡፡
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
እዛ ሰው ይሞታል፣ እዛ ደም ይፈሳል
እዚህ ይጨፈራል ፣ እዚህ ይደነሳል
እዛ ሰው ያለቅሳል፣እዚህ ሳቅ ይነግሳል።
፨፨፨
እዛም እኛዎች ነን፣አዚም እኛ ባዮች
የደላን እኛው ነን ፣ እኛው ተበዳዮች
አንድነትን ሰብከን፣የምንሆን ብዙዎች፡፡
እኛው ነን የሞትነው፣እኛው ነን ቀባሪ
እኛው ነን ሙሾ አውራጅ፣እኛው ነን ጨፋሪ
አንድ ነን እያልን ፣ ልዩነት ፈጣሪ፡፡
፨፨
እዛ እኛ ስንሞት፣ እዚ እኛ ስንጨፍር
እዛ እኛን ስንቀንስ፣እዚ እኛን ስንደምር
ሙሾን ከደስታ ጋር የምንደባልቀው
እኛው እያነባን ፣ እኛው የምንስቀው
እኛው ለነፃነት ፣ ታግለን የምናልቀው
እኛው ባርነትን፣ፈቅደን የምንሞቀው
እዚ እየረሳን ፣ እዛ ም'ናፍቀው
ፍቅር መሽቶብን ነው፡፡
፨፨
እንዲህ ነው ሚኖረው....
ፍቅር የመሸበት፣ሀቅ ያልገባው ሀገር
እዛ እኛ ሙሾ አውራጅ ፣ እኛ አዚ ምንጨፍር፡፡
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
😢20👍11👏4❤3🔥2
#እኔና_ጊዜ
ጊዜ አጥቼ እንጂ፣ ፍቅሬን ለማስረዳት
የሰማንያ ሚስቴን፣ በጣም ነው ምወዳት፡፡
ተወጥሬ እንጂ፣ ሀገሬን በማልማት
መቼ ዝም እል ነበር?፣ ልጄ ‘በራብ’ ሲሞት፡፡
ቸኩዬ ነው እንጂ፣ ስሮጥ ለቁም-ነገር
ሁለት ሰው ገጭቼ፣ አላመልጥም ነበር!!!
በተለይ በተለይ…
ጊዜ አጣሁኝ እንጂ፣ ጥቂት ፋታ ባገኝ ስለ ጊዜ ጥቅም፣ የምለው ነበረኝ !!!
#Share and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ጊዜ አጥቼ እንጂ፣ ፍቅሬን ለማስረዳት
የሰማንያ ሚስቴን፣ በጣም ነው ምወዳት፡፡
ተወጥሬ እንጂ፣ ሀገሬን በማልማት
መቼ ዝም እል ነበር?፣ ልጄ ‘በራብ’ ሲሞት፡፡
ቸኩዬ ነው እንጂ፣ ስሮጥ ለቁም-ነገር
ሁለት ሰው ገጭቼ፣ አላመልጥም ነበር!!!
በተለይ በተለይ…
ጊዜ አጣሁኝ እንጂ፣ ጥቂት ፋታ ባገኝ ስለ ጊዜ ጥቅም፣ የምለው ነበረኝ !!!
#Share and #subscribe my #YouTube
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
😁25👍8🥰5
ካንተ ቤት......
ቋንጣ ተሰቀለ
ሻኛ ተቆረጠ፣ ወይን እየተጠጣ፣
፨፨
ያ’ዳም ዘር ወንድምህ
ያለ ሁዳዴ ፆም በ’ራብ የ’ተቀጣ፡፡
፨፨
ይገርማል
አንተ ማለትኮ...
አንተ ማለት ጥጋብ ያለልክ ሠልቃጭ፣
እሱ ማለት ደግሞ...
እሱ ማለት ሚስኪን ካንተ ቤት ቀላዋጭ፣
፨፨
እንዲህ ነው ተፈጥሮ እግዜሩ ሲያዳላ፣
አንዱ ፆሙን ሲያድር ሌላኛው ሲበላ፡፡
፨፧
በተራበች ነፍሱ
........ቀልቡ እየዋለለ፣
ድህነት ሰቅዞት
.......ሳይበላ እየዋለ፣
ሂወት ጨክናበት
ቆዳ ምላሽ ሊያገኝ
..........በጌቶቹ ቅዬ ፍሪዳ እየጣለ፣
ለሁዳዴው ፆም ፍቺ
በግ ሲጠባ ያድራል ቢለዋ እየሳለ፣
፨፨
እንዲህ ነው ተፈጥሮ እግዜሩ ሲያዳላ፣
አንዱ ፆሙን ሲያድር ሌላኛው ሲበላ፡፡
፨፨
ትቀምሰው ያጣች ነፍስ ቁራሽ ንጣይ ቅምሻ፣
በጣር ሲቃ ታንቃ ስታጣ መድረሻ፣
ፍርድ አጥተን ከሰማይ የ'ግዜር እጅ መንሻ፣
ሠው የሠው አገልጋይ ሠው የመንደር ውሻ፣
ሲ..ጎ..መ..ጅ ይኖራል በ.በ.ሊ.ቶ.ች ጉርሻ፡፡
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ቋንጣ ተሰቀለ
ሻኛ ተቆረጠ፣ ወይን እየተጠጣ፣
፨፨
ያ’ዳም ዘር ወንድምህ
ያለ ሁዳዴ ፆም በ’ራብ የ’ተቀጣ፡፡
፨፨
ይገርማል
አንተ ማለትኮ...
አንተ ማለት ጥጋብ ያለልክ ሠልቃጭ፣
እሱ ማለት ደግሞ...
እሱ ማለት ሚስኪን ካንተ ቤት ቀላዋጭ፣
፨፨
እንዲህ ነው ተፈጥሮ እግዜሩ ሲያዳላ፣
አንዱ ፆሙን ሲያድር ሌላኛው ሲበላ፡፡
፨፧
በተራበች ነፍሱ
........ቀልቡ እየዋለለ፣
ድህነት ሰቅዞት
.......ሳይበላ እየዋለ፣
ሂወት ጨክናበት
ቆዳ ምላሽ ሊያገኝ
..........በጌቶቹ ቅዬ ፍሪዳ እየጣለ፣
ለሁዳዴው ፆም ፍቺ
በግ ሲጠባ ያድራል ቢለዋ እየሳለ፣
፨፨
እንዲህ ነው ተፈጥሮ እግዜሩ ሲያዳላ፣
አንዱ ፆሙን ሲያድር ሌላኛው ሲበላ፡፡
፨፨
ትቀምሰው ያጣች ነፍስ ቁራሽ ንጣይ ቅምሻ፣
በጣር ሲቃ ታንቃ ስታጣ መድረሻ፣
ፍርድ አጥተን ከሰማይ የ'ግዜር እጅ መንሻ፣
ሠው የሠው አገልጋይ ሠው የመንደር ውሻ፣
ሲ..ጎ..መ..ጅ ይኖራል በ.በ.ሊ.ቶ.ች ጉርሻ፡፡
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍24❤3😁2
💥💞#አልተዘዋወረችም💥💞
✍ አሌክስ አብርሃም
ክፍል ሠባት
“አበባም ይሁን ድንጋይ፣ በግድ እስካሸከሙን ድረስ ያው ሸክም ነው!”
ማኀደረ-ሰላም!
አገባሁ!! ድል ባለ ሰርግ ዮናስ የሚባል ከአሜሪካ የመጣ ሰው አገባሁ፡፡ አስተያዬት ሰጪዎች ግን ለባለቤቴ የሚሉት “አፈስክ” ነው። አስተፋፈሱ የየቅል ይሁን እንጂ፧ እኔም ባለቤቴ ያገባኝ ሳይሆን ያፈሰኝ ነው የሚመስለኝ፡፡ በሆነ ግዴለሽ መዳፍ! እንደ አልባሌ ነገር የትም ተበታትኜ ከተደፋሁበት አፋፍሶ ያገባኝ ነው የሚመስለኝ። ለራሴ ቢቀፈኝም ከወዳደቅሁ እኔ ገጣጥሞ፣ በወጉ ያልተቃኜች በድን ሚስት የምትባል ፍጥረት የሠራ ነው የሚመስለኝ፡፡ በድፍን አዲስ አበባ ከላፍቶ እስከ ሜክስኮ፣ ከቦሌ እስከሃያሁለትና መገናኛ፣ ከተበታተንኩበት ለቃቅሞ የገጣጠመኝ ልክ እንደተሰበረ ብርጭቆ፣ ከነስንጥቄ ተጠጋግኜ የሆነ ደግ ሰው ቤት የተቀመጥኩ፣ ውስጤ ፍቅር የማይቋጥር እንዲሁ ቅርስ ነገር ...የዕድለ ቢስነት መታሰቢያ ቅርስ። ታዲያ መልስ ሲባል ባሌ አልፈልግም ብሎ ወደ አባቴ ቤት የሚመልሰኝ መስሎ ነበር የተሰማኝ፡፡ባደረገዉ...!
ብዙ ሰዎች ሲሉ እንደሰማሁት ትዳር የአዲስ ሕይወት ጅማሬ፣ ያለፈ ታሪካችንን አጀንዳ ዘግተን ለአዲስ ነገ “ሀ” ብለን ርምጃ የምንጀምርበት ምዕራፍ መስሎኝ ነበር፡፡ ግን ለእኔ እንደዚያ አልነበረም፡፡ ያለፈ ታሪኬን፣ ትዝታዬን፣ ሕመሜንና ደስታዬን ሁሉ ልክ እንደ ልብስና ሌላ ሌላ ኮተቴ ሁሉ በአእምሮዬ ሻንጣ አጭቄ ነበር ወደ አዲሱ ቤት ያዘገምኩት፡፡ ያው አዲስ አበባ ይባል እንጂ ሩቅ ነበር ለእኔ፡፡ ሰሚት ወደ ሚባል ሰፈር፡፡ አሜሪካ ይሁን አንታርቲካ፣ ሰሚት ይሁን ቃልቲ፣ ከምወዳት ሰፈሬ ሜክሲኮ ከራቀ ሩቅ ነው፤ ሩቅ ነበር ለእኔ። ስደት በርቀት ካልተለካ በስተቀር ስደት ነበር ለእኔ፡፡ ልደታን ወረድ ብዬ ካላዬሁ ያዛጋኛል፡፡ የዋቢ ሸበሌ ሆቴልን አጥር ታክኬ ካላለፍኩ ዓለም ምልክት የሌላት ምድረበዳ ትመስለኛለች፡፡ በ'ኮሜርስ' ዙሪያ ካላንዣበብኩ አዲስ አበባ የዋልኩ አይመስለኝም፡፡ ብሔራዊ ቲአትር በር የሚለጠፉ ማስታወቂያዎችንና የቲያትር “ፖስተሮችን” ካላዬሁ፣ የዕለት መዝሙረ ዳዊቱን ሳይደግም እንደወጣ ሃይማኖተኛ ቅር ቅር ሲለኝ ይውላል፤ ስንት የማናውቀው ሱስ አለብን!? እትብት የሚባለው ነገር በሥጋ እንጂ በነፍስ አይቆረጥም መሰል!? የተወለድንበት ሰፈር ላይ ያለ የማይታይ የመንፈስ ችካል ላይ ተቋጥሮ፣ በረዥም ክር ከእኛ ጋር የተሳሰረ ነገር ነው፤ የትም ብንሄድ ይስበናል፡፡ ሻንጣዬን ከፍቼ ልብሶቼን ቦታ ቦታ ሳሲይዝ፣ አእምሮዬም በሰፊው ተከፍቶ አሮጌ ትዝታዬን በአዲሱ ቤቴ ውስጥ እንደ ፎቶ መደርደር ጀመረ፡፡ እያንዳንዱን ልብስ ለብሼ፣ ምን እንዳደረኩ አውቃለሁ፡፡ እያንዳንዷን ቀሚስ እንዴት እንደገለብኩ፣ ሱሪዎቼን በእብደት ቁልቁል እንዳንሸራተትኳቼው አውቃለሁ፡፡ ከምንወዳቼው ጋር ስንት ጊዜ ልብሳችንን አውልቀን ስንት ጊዜ ለብሰናል?...ማነው የቆጠረው? በደመነፍስ ስንት ዓይነት ፈጣን አወላለቅ ተምረናል፡፡ ገና ቀጠሮ ስንይዝ፣ ውዶቻችን ልብሳችንን ለማውለቅ እንዳይቼገሩ ቀለል ያለውን አልመረጥንም? ልብስ ብዙ ብዙ ነገር ነው፡፡ ቢታጠብም የማይለቅ አሻራ፣ ከመተቃቀፎቻችን የቀረ ጠረን ሁሉ ዘላለማዊ ነው፤ ልብሶቼን እወዳቸዋለሁ፡፡ ውድ
ቅርስ እንደሚሰበስቡ ሰዎች፣ የእኔ ሰብስቦች ልብሶቼ ነበሩ። ውድ ሆነው አይደለም የተለዬ “ብራንድ” ያላቼው ወይም በአድናቆት የት አገኘሻቼውን የሚባልላቸው አልነበሩም። ለፋሽን ግድ የለኝም፣ለውበትም ያን ያኽል አልጨነቅም፡፡ምቾታቸው ድሎቴ ነው: ውስጣቼው ኑሪያለሁ ከቤቴ፣ ከሕይወቴ፣ ከአገሬም በላይ ልብሶቼ ውስጥ ኖሪያለሁ፣ መደበቂያዎቹ ነበሩ። የእኔ የራሴ ባንዲራዎች ነበሩ፡፡ ልብሶች ተራ ነገር አይደሉም፣ የግል ባንዲራዎቻችን ናቸው፡፡ አገር ባንዲራውን፣ ሰው ልብሱን ከጣለ ምን ቀረው? ሁለቱም እብደት ነው፡፡አረጄ ብለን የምንወረውረው ልብስ፣ ልብስ ብቻ አይደለም፤ የዕድሜ አሻራችን ጭምር እንጂ፡፡ ካለነገሩ አይደለም የለበስነውን ልብስ ተመሳሳይ ሌሎች ለብሰውት ስናይ ውስጣችን በቅሬታ የሚሞላው? ሌሎች ባንዲራችንን የነጠቁን ስለሚመስለን ነው፡፡ ግድግዳው፣ ጣሪያው፣ መኝታ ቤቱ፣ ሳሎኑ፣ መታጠቢያ ቤትና ማብሰያ ቤቱ ሁሉ ቁጥር ስፍር በሌለው ትዝታዬ ተሞልቶ፣ ገና ሳምንት ሳይሞላኝ አዲሱ ቤት ዕድሜ ልኬን የኖርኩበት አሮጌ ዋሻ መስሎ ተሰማኝ፡፡ ከምንም በላይ ያመመኝ እና ያደከመኝ፣ ደስተኛ መስዬ ለመታዬት አደርገው የነበረው ጥረት ነበር። እንዴት ሰው ዕድሜውን በሙሉ ሌሎችን ለማስደሰት እና ተቀባይነት ለማግኘት ሲባዝን ይኖራል? ...እኩል ምድር፣ እኩል ሰብአዊ ክብር፣ ተሰጥቶን እንዴት ነው አንዱ ለማኝ አንዱ ተለማኝ የሚሆነው!? ባለቤቴ በአዲስ ትዳር ናውዞ ሲሟዘዝ፣ አብሬው መሟዘዝ፣ ሲስቅ- መሳቅ፣ በስሜት ሲግል፣ እሳት ላይ ቢጥዱት የማይሞቅ ቀዝቃዛ ሥጋዬን የሞቀ ለማስመሰል መጣር፣ ባል~ ባል ለመሆን ሲደክም፣ ሚስት - ሚስት ለመምሰል መፍገምገም- ብዙ ማስመሰል፤ግን ብዙ መቀጠል አልቻልኩም።
እስከ መቼ ነው እንዲህ የምኖረው!? ያልኩት ገና በሳምንቱ ነበር፤ በተጋባን በሳምንቱ። የቤተዘመዱ ዕልልታ እንኳን፣ ካንዱ ቤት ሌላው ቤት ግድግዳ የሚነጥር የገደል ማሚቱው አልጠፋም ነበር። እልልልል ሲባል አእምሮዬ ይኼ እልልታ ለማነው? ይላል። ባለቤቴ ጋር የተዋወቅነው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ ንግድ ሥራ ኮሌጅ የመጀመሪያ ድግሪዬን ሥሠራ ነበር። የዛሬን አያድርገውና ጥርስ የማያስከድን ተጫዋች ልጅ ነበር። በግሩፕ ከነበረ ጓደኝነት እንደ አንዳቼው ከማዬት ባለፈ በግል እንኳን ያን ያኽል ቅርበት አልነበረንም፡፡ እንዲያውም ጓደኛዬ ሃይሚ “ይኼ ወሬኛ መጣ''እያለች እንድንርቀው ስለምትገፋፋኝ ብዙም አልቀርበውም ነበር። ልንመረቅ እንድ ዓመት ሲቀረን፣ ምን ሰይጣን ሹክ እንዳለው እንጃ፣ ትምህርቱን አቋርጦ ወደ ሱዳን ተሰደደ ተባለ፡፡ ወሬው ከዬት እንደመጣ አላስታውስም። ሁልጊዜ ከክላስ በኋላ የማይጠፋባት ፎቶ ኮፒ ቤት የሆነ ነገር ኮፒ ላደርግ ስሄድ እግረ መንገዴን እዚያ ያገኜሁትን ጓደኛውን “ዮኒ የት ሄዶ ነው?'' ብዬ ጠየቅሁት፤ እሱም እንዳላወቀ ነገረኝ፤ ያኔ ከአንድ ሰሞን ያለፈ ወሬ አልነበረም፤ በቃ ተረሳ። እሱ እንደገና ከተገናኜን በኋላ፣ እንደነገረኝ ከሆነ ለዓመታት ብዙ ብዙ ችግር እሳልፎ አሜሪካ ገባ፡፡ አሁን ኑሮው እዚያዉ አሜሪካ ነው፡፡ ገና ሳንጋባ በግልጽ እንደነገረኝ፣ ታክሲ ይነዳል፣ የጽዳት ሥራ ይሠራል። በዚሁ ታታሪነቱ ለቤተሰቦቹም ለራሱም ተርፏል፡፡ ዮናስ ከሰርጋችን አንድ ዓመት ቀደም ብሎ ለእረፍት ወደ ኢትዮጵያ እንደመጣ ነበር ስድስት ኪሎ ውልና ማስረጃ ድንገት የተገናኜነው፡፡ የዚያን ቀን ግጥጥሞሸ ይገርመኛል፣ አለቃዬ የሆነ ፋይል እንድታመጣለት ሰናይት የምትባል ቢሮ የምትጋራኝ ሠራተኛ ሊልክ ወደ ቢሯችን ይመጣል። በአጋጣሚ ወጥታ ስለነበር ሲጨናነቅ ሳዬው “በዚያው የምሄድበት ጉዳይ ስላለኝ እኔ አመጣልሀለሁ" ብዬው ፋይሉን ላመጣ ሄድኩ፡፡
ታዲያ ፋይሉን ተቀብዬ ስወጣ ከእንግዳ ማስተናገጃው አካባቢ ስሜ ከኋላ ሲጠራ ሰምቼ ዞር ብል፣ የጠራኝ ሰው ከስንትና ስንት ዓመት በፊት የማውቀው ዮናስ ሆኖ አገኜሁት። እውነቱን ለመናገር መጀመሪያ አላስታወስኩትም _ ነበር፣ ከዕድሜው በላይ ትልቅ ሰው መስሏል፤ ሲናገር ነው ያስታወስኩት፡፡ ከኮሌጅ ጀምሮ ሲናገር ዓይኑን በከፊል ከደን የሚያደርገው ነገር ነበር፡፡ ባልሳሳት ወደ ዐሥራ አምስት ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ ሳንተያይ ቆይተን ነበር፡፡ ከዚያች ቀን ጀምሮ ነገራችን ሁሉ ፍጥንጥን
✍ አሌክስ አብርሃም
ክፍል ሠባት
“አበባም ይሁን ድንጋይ፣ በግድ እስካሸከሙን ድረስ ያው ሸክም ነው!”
ማኀደረ-ሰላም!
አገባሁ!! ድል ባለ ሰርግ ዮናስ የሚባል ከአሜሪካ የመጣ ሰው አገባሁ፡፡ አስተያዬት ሰጪዎች ግን ለባለቤቴ የሚሉት “አፈስክ” ነው። አስተፋፈሱ የየቅል ይሁን እንጂ፧ እኔም ባለቤቴ ያገባኝ ሳይሆን ያፈሰኝ ነው የሚመስለኝ፡፡ በሆነ ግዴለሽ መዳፍ! እንደ አልባሌ ነገር የትም ተበታትኜ ከተደፋሁበት አፋፍሶ ያገባኝ ነው የሚመስለኝ። ለራሴ ቢቀፈኝም ከወዳደቅሁ እኔ ገጣጥሞ፣ በወጉ ያልተቃኜች በድን ሚስት የምትባል ፍጥረት የሠራ ነው የሚመስለኝ፡፡ በድፍን አዲስ አበባ ከላፍቶ እስከ ሜክስኮ፣ ከቦሌ እስከሃያሁለትና መገናኛ፣ ከተበታተንኩበት ለቃቅሞ የገጣጠመኝ ልክ እንደተሰበረ ብርጭቆ፣ ከነስንጥቄ ተጠጋግኜ የሆነ ደግ ሰው ቤት የተቀመጥኩ፣ ውስጤ ፍቅር የማይቋጥር እንዲሁ ቅርስ ነገር ...የዕድለ ቢስነት መታሰቢያ ቅርስ። ታዲያ መልስ ሲባል ባሌ አልፈልግም ብሎ ወደ አባቴ ቤት የሚመልሰኝ መስሎ ነበር የተሰማኝ፡፡ባደረገዉ...!
ብዙ ሰዎች ሲሉ እንደሰማሁት ትዳር የአዲስ ሕይወት ጅማሬ፣ ያለፈ ታሪካችንን አጀንዳ ዘግተን ለአዲስ ነገ “ሀ” ብለን ርምጃ የምንጀምርበት ምዕራፍ መስሎኝ ነበር፡፡ ግን ለእኔ እንደዚያ አልነበረም፡፡ ያለፈ ታሪኬን፣ ትዝታዬን፣ ሕመሜንና ደስታዬን ሁሉ ልክ እንደ ልብስና ሌላ ሌላ ኮተቴ ሁሉ በአእምሮዬ ሻንጣ አጭቄ ነበር ወደ አዲሱ ቤት ያዘገምኩት፡፡ ያው አዲስ አበባ ይባል እንጂ ሩቅ ነበር ለእኔ፡፡ ሰሚት ወደ ሚባል ሰፈር፡፡ አሜሪካ ይሁን አንታርቲካ፣ ሰሚት ይሁን ቃልቲ፣ ከምወዳት ሰፈሬ ሜክሲኮ ከራቀ ሩቅ ነው፤ ሩቅ ነበር ለእኔ። ስደት በርቀት ካልተለካ በስተቀር ስደት ነበር ለእኔ፡፡ ልደታን ወረድ ብዬ ካላዬሁ ያዛጋኛል፡፡ የዋቢ ሸበሌ ሆቴልን አጥር ታክኬ ካላለፍኩ ዓለም ምልክት የሌላት ምድረበዳ ትመስለኛለች፡፡ በ'ኮሜርስ' ዙሪያ ካላንዣበብኩ አዲስ አበባ የዋልኩ አይመስለኝም፡፡ ብሔራዊ ቲአትር በር የሚለጠፉ ማስታወቂያዎችንና የቲያትር “ፖስተሮችን” ካላዬሁ፣ የዕለት መዝሙረ ዳዊቱን ሳይደግም እንደወጣ ሃይማኖተኛ ቅር ቅር ሲለኝ ይውላል፤ ስንት የማናውቀው ሱስ አለብን!? እትብት የሚባለው ነገር በሥጋ እንጂ በነፍስ አይቆረጥም መሰል!? የተወለድንበት ሰፈር ላይ ያለ የማይታይ የመንፈስ ችካል ላይ ተቋጥሮ፣ በረዥም ክር ከእኛ ጋር የተሳሰረ ነገር ነው፤ የትም ብንሄድ ይስበናል፡፡ ሻንጣዬን ከፍቼ ልብሶቼን ቦታ ቦታ ሳሲይዝ፣ አእምሮዬም በሰፊው ተከፍቶ አሮጌ ትዝታዬን በአዲሱ ቤቴ ውስጥ እንደ ፎቶ መደርደር ጀመረ፡፡ እያንዳንዱን ልብስ ለብሼ፣ ምን እንዳደረኩ አውቃለሁ፡፡ እያንዳንዷን ቀሚስ እንዴት እንደገለብኩ፣ ሱሪዎቼን በእብደት ቁልቁል እንዳንሸራተትኳቼው አውቃለሁ፡፡ ከምንወዳቼው ጋር ስንት ጊዜ ልብሳችንን አውልቀን ስንት ጊዜ ለብሰናል?...ማነው የቆጠረው? በደመነፍስ ስንት ዓይነት ፈጣን አወላለቅ ተምረናል፡፡ ገና ቀጠሮ ስንይዝ፣ ውዶቻችን ልብሳችንን ለማውለቅ እንዳይቼገሩ ቀለል ያለውን አልመረጥንም? ልብስ ብዙ ብዙ ነገር ነው፡፡ ቢታጠብም የማይለቅ አሻራ፣ ከመተቃቀፎቻችን የቀረ ጠረን ሁሉ ዘላለማዊ ነው፤ ልብሶቼን እወዳቸዋለሁ፡፡ ውድ
ቅርስ እንደሚሰበስቡ ሰዎች፣ የእኔ ሰብስቦች ልብሶቼ ነበሩ። ውድ ሆነው አይደለም የተለዬ “ብራንድ” ያላቼው ወይም በአድናቆት የት አገኘሻቼውን የሚባልላቸው አልነበሩም። ለፋሽን ግድ የለኝም፣ለውበትም ያን ያኽል አልጨነቅም፡፡ምቾታቸው ድሎቴ ነው: ውስጣቼው ኑሪያለሁ ከቤቴ፣ ከሕይወቴ፣ ከአገሬም በላይ ልብሶቼ ውስጥ ኖሪያለሁ፣ መደበቂያዎቹ ነበሩ። የእኔ የራሴ ባንዲራዎች ነበሩ፡፡ ልብሶች ተራ ነገር አይደሉም፣ የግል ባንዲራዎቻችን ናቸው፡፡ አገር ባንዲራውን፣ ሰው ልብሱን ከጣለ ምን ቀረው? ሁለቱም እብደት ነው፡፡አረጄ ብለን የምንወረውረው ልብስ፣ ልብስ ብቻ አይደለም፤ የዕድሜ አሻራችን ጭምር እንጂ፡፡ ካለነገሩ አይደለም የለበስነውን ልብስ ተመሳሳይ ሌሎች ለብሰውት ስናይ ውስጣችን በቅሬታ የሚሞላው? ሌሎች ባንዲራችንን የነጠቁን ስለሚመስለን ነው፡፡ ግድግዳው፣ ጣሪያው፣ መኝታ ቤቱ፣ ሳሎኑ፣ መታጠቢያ ቤትና ማብሰያ ቤቱ ሁሉ ቁጥር ስፍር በሌለው ትዝታዬ ተሞልቶ፣ ገና ሳምንት ሳይሞላኝ አዲሱ ቤት ዕድሜ ልኬን የኖርኩበት አሮጌ ዋሻ መስሎ ተሰማኝ፡፡ ከምንም በላይ ያመመኝ እና ያደከመኝ፣ ደስተኛ መስዬ ለመታዬት አደርገው የነበረው ጥረት ነበር። እንዴት ሰው ዕድሜውን በሙሉ ሌሎችን ለማስደሰት እና ተቀባይነት ለማግኘት ሲባዝን ይኖራል? ...እኩል ምድር፣ እኩል ሰብአዊ ክብር፣ ተሰጥቶን እንዴት ነው አንዱ ለማኝ አንዱ ተለማኝ የሚሆነው!? ባለቤቴ በአዲስ ትዳር ናውዞ ሲሟዘዝ፣ አብሬው መሟዘዝ፣ ሲስቅ- መሳቅ፣ በስሜት ሲግል፣ እሳት ላይ ቢጥዱት የማይሞቅ ቀዝቃዛ ሥጋዬን የሞቀ ለማስመሰል መጣር፣ ባል~ ባል ለመሆን ሲደክም፣ ሚስት - ሚስት ለመምሰል መፍገምገም- ብዙ ማስመሰል፤ግን ብዙ መቀጠል አልቻልኩም።
እስከ መቼ ነው እንዲህ የምኖረው!? ያልኩት ገና በሳምንቱ ነበር፤ በተጋባን በሳምንቱ። የቤተዘመዱ ዕልልታ እንኳን፣ ካንዱ ቤት ሌላው ቤት ግድግዳ የሚነጥር የገደል ማሚቱው አልጠፋም ነበር። እልልልል ሲባል አእምሮዬ ይኼ እልልታ ለማነው? ይላል። ባለቤቴ ጋር የተዋወቅነው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ፣ ንግድ ሥራ ኮሌጅ የመጀመሪያ ድግሪዬን ሥሠራ ነበር። የዛሬን አያድርገውና ጥርስ የማያስከድን ተጫዋች ልጅ ነበር። በግሩፕ ከነበረ ጓደኝነት እንደ አንዳቼው ከማዬት ባለፈ በግል እንኳን ያን ያኽል ቅርበት አልነበረንም፡፡ እንዲያውም ጓደኛዬ ሃይሚ “ይኼ ወሬኛ መጣ''እያለች እንድንርቀው ስለምትገፋፋኝ ብዙም አልቀርበውም ነበር። ልንመረቅ እንድ ዓመት ሲቀረን፣ ምን ሰይጣን ሹክ እንዳለው እንጃ፣ ትምህርቱን አቋርጦ ወደ ሱዳን ተሰደደ ተባለ፡፡ ወሬው ከዬት እንደመጣ አላስታውስም። ሁልጊዜ ከክላስ በኋላ የማይጠፋባት ፎቶ ኮፒ ቤት የሆነ ነገር ኮፒ ላደርግ ስሄድ እግረ መንገዴን እዚያ ያገኜሁትን ጓደኛውን “ዮኒ የት ሄዶ ነው?'' ብዬ ጠየቅሁት፤ እሱም እንዳላወቀ ነገረኝ፤ ያኔ ከአንድ ሰሞን ያለፈ ወሬ አልነበረም፤ በቃ ተረሳ። እሱ እንደገና ከተገናኜን በኋላ፣ እንደነገረኝ ከሆነ ለዓመታት ብዙ ብዙ ችግር እሳልፎ አሜሪካ ገባ፡፡ አሁን ኑሮው እዚያዉ አሜሪካ ነው፡፡ ገና ሳንጋባ በግልጽ እንደነገረኝ፣ ታክሲ ይነዳል፣ የጽዳት ሥራ ይሠራል። በዚሁ ታታሪነቱ ለቤተሰቦቹም ለራሱም ተርፏል፡፡ ዮናስ ከሰርጋችን አንድ ዓመት ቀደም ብሎ ለእረፍት ወደ ኢትዮጵያ እንደመጣ ነበር ስድስት ኪሎ ውልና ማስረጃ ድንገት የተገናኜነው፡፡ የዚያን ቀን ግጥጥሞሸ ይገርመኛል፣ አለቃዬ የሆነ ፋይል እንድታመጣለት ሰናይት የምትባል ቢሮ የምትጋራኝ ሠራተኛ ሊልክ ወደ ቢሯችን ይመጣል። በአጋጣሚ ወጥታ ስለነበር ሲጨናነቅ ሳዬው “በዚያው የምሄድበት ጉዳይ ስላለኝ እኔ አመጣልሀለሁ" ብዬው ፋይሉን ላመጣ ሄድኩ፡፡
ታዲያ ፋይሉን ተቀብዬ ስወጣ ከእንግዳ ማስተናገጃው አካባቢ ስሜ ከኋላ ሲጠራ ሰምቼ ዞር ብል፣ የጠራኝ ሰው ከስንትና ስንት ዓመት በፊት የማውቀው ዮናስ ሆኖ አገኜሁት። እውነቱን ለመናገር መጀመሪያ አላስታወስኩትም _ ነበር፣ ከዕድሜው በላይ ትልቅ ሰው መስሏል፤ ሲናገር ነው ያስታወስኩት፡፡ ከኮሌጅ ጀምሮ ሲናገር ዓይኑን በከፊል ከደን የሚያደርገው ነገር ነበር፡፡ ባልሳሳት ወደ ዐሥራ አምስት ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ ሳንተያይ ቆይተን ነበር፡፡ ከዚያች ቀን ጀምሮ ነገራችን ሁሉ ፍጥንጥን
👍46❤6😢2
ያለ ነበር፡፡ ያ ጊዜ የአብርሐም ነገር ያንገሸገሸብኝ፣ ሕይወትም ስልችት ብሎኝ ሥጋዬ በደመነፍስ የሚንገላወድበት ጊዜ ነበር፡፡ የሆነውን ሁሉ ከእኔ እኩል ትሰማ የነበረችው ጓደኛዬ ሃይሚ እንኳን ልንጋባ መሆኑን ያወቀችው ነገሩ ሁሉ አልቆ ለሚዜነት ስጠይቃት ነበር፡፡ አደነጋገጧ ሁሉ ትዝ ይለኛል፤ ረዘም ላለ ጊዜ ሳንገናኝ ቆይተን ምሳ ልጋብዝሸ ብዬ ቀጠርኳትና "አንድ ጥሩ አንድ መጥፎ ዜና አለኝ" አልኳት
“በናትሽ ዛሬ ጥሩ ሙድ ውስጥ አይደለሁም፣ ስለዚያ አብርሃም ስለሚባል ሰውዬሽ ምንም እንዳታወሪኝ አለችኝ'' በምሬት እየተንገሸገሸች፤
“አንዱ ስለ እሱ ነው"
“መጥፎው ዜና ስለ'ሱ ከሆነ ንገሪኝ!” ተሳሳቅንና
“ተለያዬን” አልኳት።
“ማለት?”
“በቃ ከዚህ በኋላ የእኔና የሱ ነገር አበቃ”
“ለስንተኛ ጊዜ መሆኑ ነው?" አለች፣ እያሾፈች፡፡
“ይኼ ከምር ነው!”
“እሱ ነው ያለሽ?''
“አይ! እኔ ነኝ!" “ያንችን እንኳን ተይው፤ እስከሚደውልልሸ ነው!!" “እሺ! ሁለተኛው ዜና.. ላገባ ነው ! " አልኳት። ቀና ብላ አይታኝ በሳቅ ፈረሰችና... “ማሂ! አሁን ፈቃድ ጠይቂ እና ሁለት ሰባት በራሴ ወጭ ጸበል እንሄዳለን!” “እውነቴን ነው አባባ ይሙት!" በአባባ ከማልኩ እንደማልቀልድ ታውቃለች፡፡ የያዘችውን ሹካ ከእጇ ላይ ጥላ... “ቆይ! ቆይ! አባባ ይሙት ነው ያልሽው?. የምታገቢው? ባል ከሰማይ ዘነበ በዚህ ፍጥነት?” ሌላው ሁሉ ይቆዬንና ማንን ነው "ያው በይው! ታውቂዋለሽ ፤ ከአሜሪካ የመጣ ልጅ ነው!" "እኮ! ማነው ደግሞ እሱ?" “ዮናስ! ኮሌጅ እያለን ትምህርቱን አቋርጦ ሱዳን የሄደ ልጅ... የሆነ ተጨዋች ልጅ፣ ረሳሽው?'' አፍጥጣ ስታዬኝ ቆይታ በረዥሙ ተነፈሰች። “ሱዳን የሄደው ልጅ ከአሜሪካ መጣ? እና ሊያገባሽ ነው? አንችም እሺ አልሽው እ!?'' አለችና በሽሙጥ ከንፈሯን ጠመም አድርጋ መለሰችው፡፡ ፊቷ ግን በብስጭት ተቀያይሮ ነበር። በረዥሙ ተንፍሳ የነበርንበትን ሬስቶራንት ዙሪያ በዓይኗ ቃኜችና የሆነ ነገር ልትናገር ገና ከንፈሯን ስታላቅቅ … … “ምንም አስተያዬት ምክር አልፈልግም፤ በቃ ሚዜዬ ነሸ፣ ካልፈለግሸ ደግሞ የራስሸ ጉዳይ!''አልኳት፡፡ ዝም አለች፤ዝምታዋ ግን መልሶ እኔን አስደነገጠኝ። ይኼን የተናገርሽው አንች ነሸ? በሚመስል ግርምት ትክ ብላ አዬችኝ፤ ወዲያው ዓይኖቿ ድንገት በዕንባ ተሞሉ። ተነስቼ ጠረጴዛውን ዞርኩና ከኋላዋ አቅፊያት ማለማመጥ ጀመርኩ። ገፋ አድርጋኝ ወደ መታጠቢያ ቤት ሄደች። ግራ ገብቶኝ
ወገቤን ይዠ ቆምኩ። እንደተመለሰች ኮስተር ብላ አስተናጋጁን ጠራቸዉና ሒሳባችንን ከፍላ “እንሂድ!” ብላ ቦርሳዋን አነሳች። በብልግናዬ ራሴን እየረገምኩ ተከተልኳት።በጭራሽ እንደገና አገኛታለሁ አላልኩም ነበር፤ ግን ማታ ደወለች። 15 ስልኩን ከማንሳቱ የይቅርታ መዓት አዥጎደጎድኩበት “እስቲ ዝም በይ! የደወልኩት የሚያስፈልግሽ ነገር ካለ እንድትነግሪኝ ነው፤ ሌላውን ከሰርግሽ በኋላ እናወራለን አለችኝ፤ ስልኩን እንደዘጋሁ አለቀስኩ። ሃይሚ ሚዜዬ ሆና ባገባም፤ ባልገባኝ ምክንያት እስከ ዛሬ ስለ ዮናስም ሆነ ስለ ሁኔታው አንድም ቃል ተንፍሳ አታውቅም፡ይኼ የእርሷ ባሀሪ አልነበረም። በጣም ወሬ ከመውደዷ የተነሳ አብርሃም ጋር እንደነበርኩ የማይጠየቅ ነገር ሁሉ ነበር የምትጠይቀኝ። “ሃይሚ አትባልጊ" ብዬ ካልተኮሳተርኩ በስተቀር በጭራሽ ጥያቄዋን አታቆምም። አሁን ግን “ቄሱም ዝም መጽሐፉም ዝም” ሆነ። እንዲያውም ከዚያ በኋላ የሌላትን ባሕሪ ቁጥብ ሆና ቀረች፡፡ በቀን ዐሥር ጊዜ የምትደውለው ልጅ ካገባሁ በኋላ ጠፋች፡፡ አልፎ አልፎ ለዚያውም ጉዳይ ሲኖራት ነበር የምንደዋወለው። እቤት የምትመጣውም የሆነ ዝግጅት ኖሮ ስጠራት ብቻ ነበር፤ ለዚያውም አትቆይም። ዮናስ ለሰርጋችን፣ የሦስት ወር ፈቃድ ወስዶ ነበር ከአሜሪካ የመጣው። እያንዳንዷን ቀንና ሰዓት በስስት ሲቆጥርና ከዚህ ጊዜው ላይ እያንዳንዷን ሰከንድ እኔን ለማስደሰት ባለ በሌለ አቅሙ ሲጥር፣ ለእኔ ግን ሦስት ወር እንደዘላለም ነበር የራቀብኝ፡፡ ቶሎ አልቆ ወደመጣበት እስኪመለስ ጓጉቼ ነበር፤ ለሌላ ነገር አይደለም ወደዚያ ጠቅልሎ እስኪወስደኝ ድረስ ብቻዬን መሆን ነበር ፍላጎቴ፡፡ አሜሪካ ሄጃ ኑሮዬን ለመቀዬር አይደለም!... እዚሀስ ኑሮ ምናለኝ? እንዲያውም እዚያ በበርሚል ይታለባል ከሚሉት የሰማይ ላም፣በስኒም ቢሆን እዚህ እጄ ላይ ያለው ወተት ሳይሻል ይቀራል!? መሄድ ነው የምፈልገው...መሄድ። ከዚህች አገር መራቅ። ከትዝታዬ መሸሽ።
ተወልደን ካደግንበት ምድር የሚያፈናቅሉን ጠላት ብለው የፈረጁን ብቻ አይደሉም፤ አፈቀርናቼው ብለን አፈር እንዳይነካቼው ራሳችንን ከጫማቼው ሥር ያነጠፍንላቼው ጭምር እንጂ፡፡ እንዲያውም ይኼኛው ስደት ያማል፤ እየገፉን በልባችን ይዘናቼው እንሰደዳለን፡፡ ፈጣሪ በቸርነቱ ካልገላገለን ዕድሜ ልካችንን ነፍሳችንን የሚያነቅዙ ነቀዝ ተፈቃሪዎች፡፡ ተምሪያለሁ፡፡ በአካውንቲንግ ሁለተኛ ድግሪዬን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ይዤ፣ በአዲተርነት እየሠራሁ ነበር፡፡ የገንዘብ ችግር አልነበረብኝም። የረባ ነገር ባላደርግ እንኳን ለራሴ በምፈልገው ልክ እኖራለሁ፡፡ የደረሰብኝ ነገር _ ስም የሌለው መዘበራረቅ ነው፡፡ ይኼ ነገር ወደ አእምሮ ሕመም ከፍ እንዳይል ስፈራ ነው የቆዬሁት፡፡ ብዙ ሴቶች በቀላሉ እንደ ቀልድ የሚያልፉት ነገር እንደሆነ አውቃለሁ፤ እኔ ግን አልቻልኩም፡፡ ከፍጥረቴ ልፍስፍስ ሆኜ ይሆናል፡፡ ወይም እኔ የተጋጨሁት ድንጋይና እነሱ የተጋጩት ድንጋይ ጥንካሬው ተለያይቶ አላውቅም...ብቻ ተጎድቻለሁ። ማልቀስ አልፈልግም፤ግን ሙሉ ቀን፣ ሙሉ ሌሊት ዕንባዬን አፍኜ መኖር ስቃይ ነው የሆነብኝ፡፡ ብቻዬን የምሆንበት አጋጣሚ ባገኝ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት አልቅሼ እንዲወጣልኝ እፈልጋለሁ፡፡ ከዚህ በኋላ አንዲት ጠብታ ዕንባ ውስጤ እንዳትቀር አድርጌ ማልቀስ፡፡ አንዳንዴ እመኛለሁ፣ ፋርማሲ ውስጥ የሚያስለቅስ መድኃኒት ይኖራቼው ይሆን? ልክ የእንቅልፍ ክኒን እንደሚባለው በቃ የሚያስለቅስ፡፡ ዕንባ የሚያፈስ አይደለም፣ ከልብ ስቅስቅ አድርጎ የሚያስለቅስ፣ ውስጤ ያለውን እልኽ፣ የበታችነት፣ መገፋት፣ መጠላት፣ እንደ ጨው አሟሙቶ የሚያወጣ ዕንባ የሚያጎርፍ መድኃኒት፡፡ ሴት ደግሞ ዕንባ ቸገራት? የሚል አይጠፋም፡፡ እዚህ አገር ሴት ልጅ ከመበደሏ በላይ የሚያመመው ማልቀሻ አገር ማጣቷ ነው። ድፍረቱ የለኝም እንጂ የሆነ ሆቴል ክፍል ይዠ እስኪበቃኝ ባለቅስ ደስታዬ ነበር፡፡ ሰው ክፍል ይዞ መፋቀር ብቻ ነው እንዴ!? ክፍል ይዞ ቢያለቅስ፣ ኡኡ... ቢልስ!? ...ያም ስሜት ይኼም ስሜት፡፡
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
“በናትሽ ዛሬ ጥሩ ሙድ ውስጥ አይደለሁም፣ ስለዚያ አብርሃም ስለሚባል ሰውዬሽ ምንም እንዳታወሪኝ አለችኝ'' በምሬት እየተንገሸገሸች፤
“አንዱ ስለ እሱ ነው"
“መጥፎው ዜና ስለ'ሱ ከሆነ ንገሪኝ!” ተሳሳቅንና
“ተለያዬን” አልኳት።
“ማለት?”
“በቃ ከዚህ በኋላ የእኔና የሱ ነገር አበቃ”
“ለስንተኛ ጊዜ መሆኑ ነው?" አለች፣ እያሾፈች፡፡
“ይኼ ከምር ነው!”
“እሱ ነው ያለሽ?''
“አይ! እኔ ነኝ!" “ያንችን እንኳን ተይው፤ እስከሚደውልልሸ ነው!!" “እሺ! ሁለተኛው ዜና.. ላገባ ነው ! " አልኳት። ቀና ብላ አይታኝ በሳቅ ፈረሰችና... “ማሂ! አሁን ፈቃድ ጠይቂ እና ሁለት ሰባት በራሴ ወጭ ጸበል እንሄዳለን!” “እውነቴን ነው አባባ ይሙት!" በአባባ ከማልኩ እንደማልቀልድ ታውቃለች፡፡ የያዘችውን ሹካ ከእጇ ላይ ጥላ... “ቆይ! ቆይ! አባባ ይሙት ነው ያልሽው?. የምታገቢው? ባል ከሰማይ ዘነበ በዚህ ፍጥነት?” ሌላው ሁሉ ይቆዬንና ማንን ነው "ያው በይው! ታውቂዋለሽ ፤ ከአሜሪካ የመጣ ልጅ ነው!" "እኮ! ማነው ደግሞ እሱ?" “ዮናስ! ኮሌጅ እያለን ትምህርቱን አቋርጦ ሱዳን የሄደ ልጅ... የሆነ ተጨዋች ልጅ፣ ረሳሽው?'' አፍጥጣ ስታዬኝ ቆይታ በረዥሙ ተነፈሰች። “ሱዳን የሄደው ልጅ ከአሜሪካ መጣ? እና ሊያገባሽ ነው? አንችም እሺ አልሽው እ!?'' አለችና በሽሙጥ ከንፈሯን ጠመም አድርጋ መለሰችው፡፡ ፊቷ ግን በብስጭት ተቀያይሮ ነበር። በረዥሙ ተንፍሳ የነበርንበትን ሬስቶራንት ዙሪያ በዓይኗ ቃኜችና የሆነ ነገር ልትናገር ገና ከንፈሯን ስታላቅቅ … … “ምንም አስተያዬት ምክር አልፈልግም፤ በቃ ሚዜዬ ነሸ፣ ካልፈለግሸ ደግሞ የራስሸ ጉዳይ!''አልኳት፡፡ ዝም አለች፤ዝምታዋ ግን መልሶ እኔን አስደነገጠኝ። ይኼን የተናገርሽው አንች ነሸ? በሚመስል ግርምት ትክ ብላ አዬችኝ፤ ወዲያው ዓይኖቿ ድንገት በዕንባ ተሞሉ። ተነስቼ ጠረጴዛውን ዞርኩና ከኋላዋ አቅፊያት ማለማመጥ ጀመርኩ። ገፋ አድርጋኝ ወደ መታጠቢያ ቤት ሄደች። ግራ ገብቶኝ
ወገቤን ይዠ ቆምኩ። እንደተመለሰች ኮስተር ብላ አስተናጋጁን ጠራቸዉና ሒሳባችንን ከፍላ “እንሂድ!” ብላ ቦርሳዋን አነሳች። በብልግናዬ ራሴን እየረገምኩ ተከተልኳት።በጭራሽ እንደገና አገኛታለሁ አላልኩም ነበር፤ ግን ማታ ደወለች። 15 ስልኩን ከማንሳቱ የይቅርታ መዓት አዥጎደጎድኩበት “እስቲ ዝም በይ! የደወልኩት የሚያስፈልግሽ ነገር ካለ እንድትነግሪኝ ነው፤ ሌላውን ከሰርግሽ በኋላ እናወራለን አለችኝ፤ ስልኩን እንደዘጋሁ አለቀስኩ። ሃይሚ ሚዜዬ ሆና ባገባም፤ ባልገባኝ ምክንያት እስከ ዛሬ ስለ ዮናስም ሆነ ስለ ሁኔታው አንድም ቃል ተንፍሳ አታውቅም፡ይኼ የእርሷ ባሀሪ አልነበረም። በጣም ወሬ ከመውደዷ የተነሳ አብርሃም ጋር እንደነበርኩ የማይጠየቅ ነገር ሁሉ ነበር የምትጠይቀኝ። “ሃይሚ አትባልጊ" ብዬ ካልተኮሳተርኩ በስተቀር በጭራሽ ጥያቄዋን አታቆምም። አሁን ግን “ቄሱም ዝም መጽሐፉም ዝም” ሆነ። እንዲያውም ከዚያ በኋላ የሌላትን ባሕሪ ቁጥብ ሆና ቀረች፡፡ በቀን ዐሥር ጊዜ የምትደውለው ልጅ ካገባሁ በኋላ ጠፋች፡፡ አልፎ አልፎ ለዚያውም ጉዳይ ሲኖራት ነበር የምንደዋወለው። እቤት የምትመጣውም የሆነ ዝግጅት ኖሮ ስጠራት ብቻ ነበር፤ ለዚያውም አትቆይም። ዮናስ ለሰርጋችን፣ የሦስት ወር ፈቃድ ወስዶ ነበር ከአሜሪካ የመጣው። እያንዳንዷን ቀንና ሰዓት በስስት ሲቆጥርና ከዚህ ጊዜው ላይ እያንዳንዷን ሰከንድ እኔን ለማስደሰት ባለ በሌለ አቅሙ ሲጥር፣ ለእኔ ግን ሦስት ወር እንደዘላለም ነበር የራቀብኝ፡፡ ቶሎ አልቆ ወደመጣበት እስኪመለስ ጓጉቼ ነበር፤ ለሌላ ነገር አይደለም ወደዚያ ጠቅልሎ እስኪወስደኝ ድረስ ብቻዬን መሆን ነበር ፍላጎቴ፡፡ አሜሪካ ሄጃ ኑሮዬን ለመቀዬር አይደለም!... እዚሀስ ኑሮ ምናለኝ? እንዲያውም እዚያ በበርሚል ይታለባል ከሚሉት የሰማይ ላም፣በስኒም ቢሆን እዚህ እጄ ላይ ያለው ወተት ሳይሻል ይቀራል!? መሄድ ነው የምፈልገው...መሄድ። ከዚህች አገር መራቅ። ከትዝታዬ መሸሽ።
ተወልደን ካደግንበት ምድር የሚያፈናቅሉን ጠላት ብለው የፈረጁን ብቻ አይደሉም፤ አፈቀርናቼው ብለን አፈር እንዳይነካቼው ራሳችንን ከጫማቼው ሥር ያነጠፍንላቼው ጭምር እንጂ፡፡ እንዲያውም ይኼኛው ስደት ያማል፤ እየገፉን በልባችን ይዘናቼው እንሰደዳለን፡፡ ፈጣሪ በቸርነቱ ካልገላገለን ዕድሜ ልካችንን ነፍሳችንን የሚያነቅዙ ነቀዝ ተፈቃሪዎች፡፡ ተምሪያለሁ፡፡ በአካውንቲንግ ሁለተኛ ድግሪዬን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ይዤ፣ በአዲተርነት እየሠራሁ ነበር፡፡ የገንዘብ ችግር አልነበረብኝም። የረባ ነገር ባላደርግ እንኳን ለራሴ በምፈልገው ልክ እኖራለሁ፡፡ የደረሰብኝ ነገር _ ስም የሌለው መዘበራረቅ ነው፡፡ ይኼ ነገር ወደ አእምሮ ሕመም ከፍ እንዳይል ስፈራ ነው የቆዬሁት፡፡ ብዙ ሴቶች በቀላሉ እንደ ቀልድ የሚያልፉት ነገር እንደሆነ አውቃለሁ፤ እኔ ግን አልቻልኩም፡፡ ከፍጥረቴ ልፍስፍስ ሆኜ ይሆናል፡፡ ወይም እኔ የተጋጨሁት ድንጋይና እነሱ የተጋጩት ድንጋይ ጥንካሬው ተለያይቶ አላውቅም...ብቻ ተጎድቻለሁ። ማልቀስ አልፈልግም፤ግን ሙሉ ቀን፣ ሙሉ ሌሊት ዕንባዬን አፍኜ መኖር ስቃይ ነው የሆነብኝ፡፡ ብቻዬን የምሆንበት አጋጣሚ ባገኝ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት አልቅሼ እንዲወጣልኝ እፈልጋለሁ፡፡ ከዚህ በኋላ አንዲት ጠብታ ዕንባ ውስጤ እንዳትቀር አድርጌ ማልቀስ፡፡ አንዳንዴ እመኛለሁ፣ ፋርማሲ ውስጥ የሚያስለቅስ መድኃኒት ይኖራቼው ይሆን? ልክ የእንቅልፍ ክኒን እንደሚባለው በቃ የሚያስለቅስ፡፡ ዕንባ የሚያፈስ አይደለም፣ ከልብ ስቅስቅ አድርጎ የሚያስለቅስ፣ ውስጤ ያለውን እልኽ፣ የበታችነት፣ መገፋት፣ መጠላት፣ እንደ ጨው አሟሙቶ የሚያወጣ ዕንባ የሚያጎርፍ መድኃኒት፡፡ ሴት ደግሞ ዕንባ ቸገራት? የሚል አይጠፋም፡፡ እዚህ አገር ሴት ልጅ ከመበደሏ በላይ የሚያመመው ማልቀሻ አገር ማጣቷ ነው። ድፍረቱ የለኝም እንጂ የሆነ ሆቴል ክፍል ይዠ እስኪበቃኝ ባለቅስ ደስታዬ ነበር፡፡ ሰው ክፍል ይዞ መፋቀር ብቻ ነው እንዴ!? ክፍል ይዞ ቢያለቅስ፣ ኡኡ... ቢልስ!? ...ያም ስሜት ይኼም ስሜት፡፡
ይቀጥላል...
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
👍46❤4👎2🔥2😢1