አትሮኖስ
286K subscribers
121 photos
3 videos
41 files
572 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ቆንጅዬ
:
#በሕይወት_እምሻው
:
#ክፍል_ሁለት
:
:
... ''ወይኔ... ወይኔ! ኸረ በማርያም ቀስ በይ...ሥጋዬን እንዳትቦጭቂው!'' አልኩ በጩኸት።

ከዚያ ቁንጅናውን ይዞ ከአዲሱ መሥርያ ቤቴ ሊለቅ ለተዘጋጀው፣ ''ቀሚስሽ ያምራል ሽሮ ልጋብዝሽ...'' ምናምን ብሎ ላሽኮረመመኝ፣ የመጀመርያው ወንድ ልጅ እራት እየተዘጋጀው ነው። የእግሮቼን ፀጉሮች በሞቀ ሰም እያስላጨሁ ነው።

ከብስጭት የተሰራ የሚመስል ፊት ያላት ሴትዬ ናት፣ ያለርህራሄ የምትላጨኝ።ሕመሙን መግለፅ አይቻልም። መጀመርያ ለፕላስተርነት ከሚቀርብ ነገር የተሰራውን ፤ በአራት-አራት መአዘን የተቆራረጠ ነገር ታመጣለች። ከዚያ ምድጃ ለይ የተጣደው ሰም ውስጥ ትከተዋለች። ደቂቃ ቆይታ ታወጣዋለች። ጸጉራሙን ቦታ እየመረጠች አንዴ ባቴ፣ አንዴ ቁርጭምጭምቴ አካባቢ፣ ሲላት ጉልበቴ ጋር ትለጥፈዋለች። ይይዛል። ይሄን ግዜ ይሞቃል እንጂ አያምም። ከዛ ግን የጭቃ ጅራፎን ታመጣዋለች። በአንድ ምት ጫፉን ይዛ ላጥ አድርጋ ስታነሳው ፣ ፀጉሬን ይዞ ሲነሳ፣ ከነቆዳዬ፣ ከነስጋዬ የተነሣ ይመስል፣ ነፍሴን ከሥጋዬ የሚያላቅቅ ሕመም ይሰማኛል። ከዛ ይሄንኑ ዐሥሬ አሥራ አንዴ፣ አሥራ ሁለቴ ትደጋግመዋለች። ህመሙን መገለፅ አይቻልም። በትንሹ ሊገልፀው የሚችለው ነገር፣ እሳት በተነከረ አለንጋ እነደመገረፍ ያለ ነው ብላችሁ ነው።

አንዱን የለጠፈችውን ላ...ጥ አድርጋ ባነሳች ቁጥር፣ ወይኔ፣ ወይኔ፣ ኸረ ቀስ ብዬ እጮሀለው።

''የመጀመርያሽ ነው?'' አለችኝ ፊቷን እንዳቀጨመች።

''አዎ...''

ዝም አለች።

''ሥጋዬም አብሮ የተነሳ ያህል ነው የሚያመኝ...'' አልኩ ሰውነቴ እየተንቀጠቀጠ። ቀጥላ የምታነሳው የትኛውን ይሆን በሚል ስጋት ተወጥሬ።

''ሲያጌጡ ይመላለጡ ነው እንግዲህ...'' አለችና ላ...ጥ ! ቀላል እየተላላጥኩ ነው?

ሴቶች ግን ምን ሆነው ራሳቸው ላይ እንዲህ አይነት ሥቃይ የሚያበዙት? ቅንድብ ሲቀነደቡ እዬዬ! ካስክ ሲገቡ መቃጣል፣ ዋክስ ሲደረጉ ስቃይ ....ምን ሆነን ነው?

ቁርጭምጭሚቴ ጋር ላ....ጥ! አደረገችኝ።

''ወይኔ .... አረ ይሄ ነገር ማደንዘዣ ያስፈልገዋል...! አልኩ።
''ሃሃ...'' አለች ፊቷ ሳይፈታ፣ ጥርሷ ሳይታይ። ምን አይነት ሳቅ ነው? መአከላዊ ገራፌ የነበረችና በሰው ስቃይ የምትደሰት ዓይነት ሰው ትመስላለች
ላ....ጥ!

''አይዞሽ ጨርሻለው አሁን...''

ጥርሶቼን እንደበረደው ሰው እያንገጫገጭኩ ፣ ዐይኖቼን ጨፍኜ እንድትጨርስ ተመኘሁ።

''አሁን ይሻላል.... ሌላ ግዜ እንደዚህ አትቆዬ...ባደገ ቁጥር ይባስ ያማል....'' አለችኝ! ፎጣዬን ያለ ፍቃዴ እስከ እንትኔ ድረስ ከፍ አድርጋ። ''ሱሪ አድርገሽ አይመችም'' ብለው አስወልቀውኝ፣ የእነሱን ፎጣ አገልድሜ በውስጥ ሱሪ ነው ያለሁት። ክው ብዬ ፎጣውን በእጆቼ ልመልስ ስል፣

''እንዴ...ምንድነው የሚታየኝ እዛ ጋር....? ደን እያለማሽ ነው እንዴ?'' አለችኝ(ገራፊዋ ቀልድም ትችላለች)። ሣቅኩ።

''እውነት ምንድን ነው እንደዚህ መዝረክረክ...አንድ በይው እንጂ....''አለችኝ እንደተኮሳተረች።

''እህ...'' አልኩ (እሱም አለ ለካ)

''ብራዚሊያን አትፈልጊም? '' አለችኝ በተኛሁበት ቁልቁል እያየችኝ። ''ብራዚሊያን ደሞ ምንድን ነው?'' አልኳት በፍርሃት እያየኋት።

'' ሆ....ያዲስ አበባ ልጅ አደለሽም እንዴ?''

''ነኝ ግን ሰምቼው አላውቅም።''

ነገረችኝ።

''እንዴ! ሴቱ እሱንም ከፍሎ ያስላጫል እንዴ?'' አልኩኝ፣ ከልክ በላይ ደንግጬም፣ ተገርሜም።

''ድብን አርጎ ነዋ...እንኳን ሴቱ ወንዱም ጀምሮል አሁንማ...'' ማመን አልቻልኩም።

(ወንድ ልጅ እዛ ጋር ያለውን ጸጉር ያስለጫል ? ለምን? ታየኝ አንዴ ወደ ግራ...አንዴ ወደ ቀኝ እያደረጉ ሲላጮዋቸው...የፈጣሪ ያለህ)

''እኛ ወንድ አንሰራም...ሴት ግን እንሰራለን...'' አለችኝ።
''እ...'' አልኩ እያቅማማሁ። እግሬን እንዲህ ያመመኝ ፣ ሥሥ ''ብልቴ'' ቢነካ ምን ልሆን እንደምችል አስቤ።
''ከእግር ብዙ አያምም...'' አለችኝ ሐሳቤን የሰማች ይመስል።

''ግን...ለምን ይላጫል ሴቱ...ማለቴ፣ቤታቸው... እራሳቸው በምላጭ ነካ ነካ...ላጨት ላጨት አያደርጉትም?''

በዚያ ፊቷ ፈገግ ማለት የምትችለውን ያህል ፈገግ ብላ፣ ''አይ...በምላጭ ለዛውም ራስሽ ፣ አይመችም እኮ...ሴቱ ደሞ እየወፈረ ቦርጩ ከልሎት እንትናቸውን ካዩ ዘመን ያለፈባቸውም ስንት አሉ እኮ...'' አለች። (ይህቺ ሴትዮ ቀላል ትቀልዳለች እንዴ...) በጣም ሳቅኩ።
''የዛሬ ወንዶች እዛ ጋር ጸጉር ሲበዛ አይወዱም አሉ....እኔ ምን ዐውቃለሁ ...ሴቶቹ እንደዛ ይሉኛል...በወር...በወር እየመጡ ዋክስ የሚያደርጉ ከስተመሮች አሉኝ።

(የዛሬ ወንዶች እዛ ጋር ጸጉር አይወዱም?...እና... ለሽሮ እራት እንትኔን በሞቀ ሰም ላስላጭ?)

''ለምንድን ነው የማይወዱት?'' አልኳት።

''እንጃ...ስንፍና ይሆናላ!...ፈልጎ ላለማግኘት..ሃሃሃ (ሆሆይ ምን ጣጣ ውስጥ ገባሁ...?)

''ስንት ብር ነው?'' አልኩ! በተኛሁበት እያየኋት።
''ከላይ ከላይ ከሆነ 300 ብር...ብራዚሊያን 500 ብር ነው። እንደኔ ግን ብራዚሊያኑ ይሻልሻል። ጥርት ያለ ነው ፣ በዛ ላይ ይቆይልሻል (ከላይ ከላይ የቱ ጋር ነው...?ብራዚሊያንስ ምን ምንን ነው የሚያካትተው ብዬ ለመጠየቅ ፈለኩ )

ቡራዚሊያን ሲሆን አንዲት ፀጉር አትቀርም...በየትም በኩል...''(ሐሳቤን ትሰማለች ልበል?)

''እሺ... ብራዚሊያን ይሁንልኝ...'' አልኩኝ፣ እየፈራሁም ፣ አዲስ ነገር ለማድረግ በመዘጋጀቴም በራሴ እየኮራሁ።

እሷ፣ አዳዳዲስ ፕላስተሮች ሰፋ ያለ ድስት ውስጥ የሚንተከተክ ሰም ውስጥ ስትነክር ፣ እኔ ለመጀመርያ ጊዜ ከፀጉር ነፃ የሆኑ እግሮቼን እርስ በእርስ አነካካሁ። አወይ መለስለሳቸው።ያማርኩ መሰለኝ።

''እሺ....እንጀምር...'' (ከመቼው ሞቀላት?)

''እሺ.... አልኩ ደንበር ብዬ...''?

''እ...ፓንትሽን አውልቅያ ...! አወለቅኩ።

''እግርሽን ወደ ላይ!'' አዘዘችኝ። የፈጣሬ ያለህ!

ከእኔ በቀር ማንም ነክቶት የማያውቅ ጓዳ ጎድጓዳዬን በረብራ አንዲት ፀጉር እንኳን ለወሬ ነገሪነት ሳታስቀር ላጭታ ጨረሰች ።

በረደኝ።

''ዕይ....ው!'' አለችና የፊት መስታወት ሰጠችኝ።

''እ...?'' አልኩ ደንግጬ።

''ዕይው ...ቅር ያለሽ ቦታ ካለ...'' (ወይ ጉድ! ምኑ ቅር ይለኛል?) ዐየሁት ሞልጫኝ የለ እንዴ! ገና ከማህፀን የወጣች አራስ ሴት ልጅ መስያለው።

''አሪፍ ነው?'' አለችኝ፣ መስታወቱን ልትቀበለኝ እየተዘጋጀች።

''አ...አዎ...'' መስታወቱን እየመለስኩላት።

''በሚቀጥለው ስትመጪ ዲዛይን እሰራልሻሀው..''

''እ?..''

''ዲዛይን....የልብ ቅርፅ ምናምን...''

ወይ ጉድ...!

''እሺ...''አልኩ እየተነሳሁ። ገላዬ የኔ አልመስል አለኝ። የተከፋፈትኩ መሰለኝ። መስኮቱም በሩም እንደተከፈተ ቤት ፣ ንፋስ ተመላለሰብኝ...ሱሪዬን ፍለጋ ዞር ስል ፣

''በይ ይልመድብሽ...እርገጠኛ ነኝ ይወደዋል..''

ትታኝ ሄደች።

የሚያየው ወንድ እንደሌለና፣ በምናልባት ከታየ፣ በዚህ ሁሉ ስቃይ እንዳለፍኩ እንደማያውቅ ብታቅ ታዝንልኝ ይሆን።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍21
አትሮኖስ pinned «#ቆንጅዬ : #በሕይወት_እምሻው : #ክፍል_ሁለት : : ... ''ወይኔ... ወይኔ! ኸረ በማርያም ቀስ በይ...ሥጋዬን እንዳትቦጭቂው!'' አልኩ በጩኸት። ከዚያ ቁንጅናውን ይዞ ከአዲሱ መሥርያ ቤቴ ሊለቅ ለተዘጋጀው፣ ''ቀሚስሽ ያምራል ሽሮ ልጋብዝሽ...'' ምናምን ብሎ ላሽኮረመመኝ፣ የመጀመርያው ወንድ ልጅ እራት እየተዘጋጀው ነው። የእግሮቼን ፀጉሮች በሞቀ ሰም እያስላጨሁ ነው። ከብስጭት የተሰራ…»
#ቆንጅዬ
:
#በሕይወት_እምሻው
:
#ክፍል_ሦስት
:
:

.... ''ውይ ዛሬ ደግሞ ሌላ ሆነሻል....እንዴት እንዳማረብሽ....'' አለኝ፣ ገና እንደተገናኘን።

ቀድሞ ደረሶ እየጠበቀኝ ነበር። ግርግር የበዛበት ምግብ ቤቱ ደንገዝገዝ ያለ ነው ። እንደውም ለጨለማ የቀረበ ነው። ተበሳጨሁ። ይሄን ሁሉ ተሰቃይቼ ውጤቱን ማሳየት የማልችልበት ቤት ይቀጥረኛል ? ስቃዬ የባከነ መሰለኝ።

''እውነት ልዩ ሆነሻል ዛሬ...'' (ህእ! ያለፍኩትን ስቃይ ባየህ!) እንደነገሩ ጉንጭ ለጉንጭ ተሳሳምንና እግሮቼን አነባብሬ ቁጭ አልኩ። አወይ አለሳለስ! አጭር ቀሚሴ ይበልጥ አጥሮ ስንት ያየሁባቸው እግሮቼና ግማሽ ጭኖቼ ተጋለጡ።

''ቤቱን ወደድሽው?'' አለ ፣ ጭኖቼን ያላየ ለመምሰል እየሞከረ። ''አዎ...ደስ ይላል።'' (ግን በጣም ጨለማ ነው...ምን ዋጋ አለው...)

''እሺ.... ስራ እንዴት ነው?''

''ደህና...ነው።''

''እየለመድሽ ነው ?''

''ምንም አልል...''

የተነባበሩት እግሮቼን ስነጣጥላቸው ከየት መጣ ያላልኩት ብርድ ቀጥ ቦሎ ማሕፀኔ ውስጥ የገባ መሰለኝ። መልሼ አነባበርኳቸው።

የተወራለት ሽሮ መጥቶ መብላት ጀመርን።

''ሽሮው እንዴት ነው ?''

''በጣም አሪፍ ነው።''

''አላጋነንኩም አይደል?'' እንጀራ ጠቅልሎ እየጎረሰ

''በጭራሽ በጣም ይጣፍጣል'' አልኩ፣ አንድ ጎርሼ እየተቅለሰለስኩ።

''ከኔ ግን አይበልጥም...''

(ዛሬም ትን ሊለኝ ነበር።ኧረ ፍጥነት ፣ በዚ አይነት እዚያ ጋር መላጨቴ ደግ ኘድርጌለሁ።)

ዝም ብዬ ጉርሻየን ማላመጥ ቀጠልኩ።

''ምነው ?'' አለኝ።

''ምነው?'' መለስኩ።

''አጠፋው እንዴ?'' (ኧረ አላጠፋክም። የኔ ሰፈፍ የሌለው ማር...የኔ ጌታ)

''አይ...''

በልተን ጨርሰን ወጣን።
:::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::
ዛሬም እንደወትሮ ተቀጣጥረን ተገናኝተናል። ከተገናኘን ጀምሮ በሳምንት ቢያንስ ሦስት ግዜ እንገናኛለን። ጸጉሬ አልበቀለም። ቀሚሴም አጭር ነው።ጸጉሬም ይተኮሳል።ከንፈሬም ቀለም ይቀባል። ግን ከ ''ዛሬ አምሮብሻል አንዳንድ ገፋ ያሉ ማባበሎች፣ መለጠፎች፣ መነካቶች ውጪ ምንም አልተፈጠረም። ምንም አልሆነም።

እስከዛሬ ለምን አልተሳሳምንም?

አልወደደኝም?

''ምንድን ነው የምታስቢው?'' አለኝ።

''ምንም...''

''ካንቺ በጣም የምወደው ነገር ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ? (ምን የኔ ጌታ.....ምን?)

''በጣም ስማርት ነሽ....(ስማርት ፊት.....ካልጠፋ ካልጠፋ ነገር ማንም የሚለኝን ነገር ይለኛል....? ይሄን ሁሉ ሆኜለት ጎበዝ ብቻ ብሎኝ ያልፋል?) መላ ሰውነቴ ኩምሽሽ አለ።

''ታንክስ....'' አልኩ የግዴን።

''ዛሬ ምሽቱ ደስ ይላል...ለምን ትንሽ ወክ አናደርግም?'' አለኝ፣ ብርጭቆው ውስጥ የቀረችውን እንጥፍጣፊ ማክያቶ ጨልጦ። ተነስተን ወጣን።የሚገርም ምሽት ነበር እውነትም ለመሳሳም የተሰራ ምሽት። ትልቅ ጨረቃ፣ ንፋስ የሌለው ግን ቀዝቀዝም፣ ለብም ያለ ውብ አየር። ሰው ያልበዛበት ዛፋም መንገድ። (አረ ሳመኝ በናትህ!)

''ሴት ልጅ ስማርት ስትሆን ደስ ይለኛል....''(እግሬን አላየም ? ቅርፄን አያይም?...ይሄንን ኬክ ወጥቄ ወጥቄ ሆዴ ተንቀርፍፏል እንዴ?)

''ቀስ በል...በሂል መሄድ አልለመድኩም አልኩት።ወሬውን ከስማርትነቴ ለመቀየር...

''ደከመሽ..?''

''እ...ትንሽ....''

''ኡፍ ግን በጣም አምሮብሻል....አለባበስ ደግሞ ስታውቂበት...''(እንዲህ ነው ወሬ....!)

''እውነት?...'' አልኩት ዞር ብዬ እያየሁት።
(ጎበዝ ነሽ ከመባል ውጪ ከወንድ ያገኘሁት የመጀመርያ አድናቆት ነው.....)

''እና ደግሞ ይሄ ቀሚስ....ይቅርታ ግን ሰውነትሽ..''
(ኧረ ይቅርታ አያስፈልግም። አወድሰኝ የኔ ጌታ...እስኪ ነጋ...ክርስቶስ እስኪመጣ አቁመህ አወድሰኝ...አድናቆት የተጠማች የሴት ነፍሴን፣ ደግመህ ደጋግመህ እያወደስክ አረስርሳት...)

''ሰውነትሽ በጣም ያምራል....''(የቱ ጋር የኔ ጌታ? ዘርዘር አድርገዋ...እግሬ ነው....ቂጤ ነው....ዐይኔ ነው... ወይስ ፀጉሬ በትንልኛ የኔ ጌታ...ቅኔ ተቀኝልኝ....!)

''እውነት?'' አልኩኝ።

''በጣም....በተለይ እግሮችሽ....''

''እግሬ ብቻ ነው ደስ የሚልህ ?'' እጁን ጨብጬ ጠየኩት።

አልቦታል።

''ኧረ....ኖ.... ፊትሽ.... ፀጉርሽ... በጣም ቆንጆ ነሽ ...'' ልቤ ምንጃርኛ ጨፈረ።( በጣም ቆንጆ ነሽ ነው ያለው ወይስ ጆሮዬ ነው?)

እጁን የበለጠ አጥብቄ ያዝኩት። (የቅንድቤና የእግሮቼ ውበት እመቤት...ያቺ ባለ ዋክስ ሴትዮ ትመስገን። ደሞዝ ይጨመርላት። ከስተመር ይብዛላት። አሜን።)

''ብዙ ሰው ግን እህቴን ነው ቆንጆ ናት የሚለው..''

''አላምንም...እህትሽ ሰላም ተስፋዬ ምናምን ካልሆነች አላምንም...ብትሆንም አንቺ ጥግ አትደርስም።'' (ሰዎች...ሰከርኩ። በቃላት ብስብስ ብዬ ሰከርኩ....)

''ፎቶዋን ብታይ እንዲህ አትልም....'' እጆቹን ጭምቅ እንዳደረኩ።

''አሳይኛ...''

ቆምኩና ስልኬን ከፈትኩ።

የእህቴን ፎቶዎች አሳየሁት።

''ኧረ በናትሽ ጫፍሽ አትደርስም!'' አለ።

''ባክህ አትፎግረኝ....በጣም ታምራለች....'' ስልኬን ቦርሳዬ እየከተትኩ መለስኩለት።

''በርግጥ ቆንጆ ናት...ማለት ሁሉ ነገሯ ለየብቻው ሲታይ ጥሩ ነው ግን...እንዳነቺ ደም ግባት የላትም....አንቺ እኮ...አንቺ እኮ...በጣም ሴኪሲ ነሽ....''

ፀጉር አልባ እግሮቼ ተንቀጠቀጡ። ሙልጭ ተደርጋ ከተላጨችው የሴትነት ሽንቁሬ ወንዝ ቢጤ መፍሰስ ጀመረ። ቆም አልኩና ተጠጋሁት።

ሳምኩት።

ከንፈሩን ግጥም አድርጌ ሳምኩት።

አንዳንድ ሴቶች በቁርጥ ስጋና ቱርቦ ተደልለው ወደ አልጋ ይሄዳሉ። አንዳንዶቹ ውድ ሽቶ ሲሰጣቸው፤ ገና ሳይቀቡት ልብሳቸውን ለሰጭያቸው ያወልቃሉ። አንዳንዶቹ ለቪትዝ የውስጥ ሱሪያቸውን ያስዘልቃሉ። አንዳንዶቹ ጂ ፕላስ ምናምን ቤት ሲያዩ ጭኖቻቸው ይከፈታሉ። አንዳንዶቹ ላሳቃቸው ወንድ ገላቸውን ይቸራሉ።

የእኔ ምስ ግን አንድ ነው፤ ''ቆንጅዬ'' መባል ''የኔ ቆንጆ'' መባል።....

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍31
አትሮኖስ pinned «#ቆንጅዬ : #በሕይወት_እምሻው : #ክፍል_ሦስት : : .... ''ውይ ዛሬ ደግሞ ሌላ ሆነሻል....እንዴት እንዳማረብሽ....'' አለኝ፣ ገና እንደተገናኘን። ቀድሞ ደረሶ እየጠበቀኝ ነበር። ግርግር የበዛበት ምግብ ቤቱ ደንገዝገዝ ያለ ነው ። እንደውም ለጨለማ የቀረበ ነው። ተበሳጨሁ። ይሄን ሁሉ ተሰቃይቼ ውጤቱን ማሳየት የማልችልበት ቤት ይቀጥረኛል ? ስቃዬ የባከነ መሰለኝ። ''እውነት ልዩ ሆነሻል…»
#ቆንጅዬ
:
#በሕይወት_እምሻው
:
#ክፍል_አራት (የመጨረሻ ክፍል)
:
:

....የእኔ ምስ ግን አንድ ነው ''ቆንጅዬ'' መባል ''የኔ ቆንጆ'' መባል።ከእህትሽ ታምሪያለሽ ብሎኝ አብሬው ያለሁት የመጀመርያ ቦይፍሬንዴ ፣ ለአልጋ ዝግጁ የሚያደርገኝን ቃል ጠንቅቆ ያውቀዋል። ወደ አልጋ ሊያስገባኝ ሲፈልግ ውድ ምሳ፣ ወይ የሻማ እራት አይጋብዘኝም። ወይን አያጠጣኝም። ስጠቶ አሽጎ አያመጣልኝም።

''ቆንጅዬ'' ሲለኝ ፍንክንክ እላለዉ። ''የኔ ውብ'' ሲለኝ ወከክ እላለሁ። ''የኔ ቆንጆ'' ሲለኝ ሙክክ ብዬ እበስላለው። ''ካንቺ በላይ ቆንጆ የለም'' ሲለኝ ሲራገብ እንደዋለ ክሰል ትርክክ እላለሁ። እንኳን ጭኖቼ ሁለንተናዬ ይከፈታል። ብርግድግዴ ይወጣል።

ቆንጆ መባሉ እኔም እንደሴቱ ወግ ደርሶኝ ቦይ ፍሬንድ ኖሮኝ ፤ የአልጋ ላይ ንግስት መሆንን ብቻ አደቸም የሰጠኝ። እሱ ቆንጆ ባለኝ ቁጥር ተጨማሪ የራስ መተማመን በመርፌ እንደተወጋ ሰው ያደርገኛል። እነቃለሁ። እነሳለሁ። ወደ ፊት እራመዳለሁ።

ቆንጅዬ ሲለኝ የደስታ ክትባት እንደተከተብኩ ሁሉ ሁለንተናዬ እየሣቀ፣ እየፈነጠዘ፣ እየተፍነከነከ በኔን ጀምሬ እጨርሰዋለሁ።

ያኔ ነው አለምም በራሳቸው ለሚተማመኑ የምትመች ቦታ መሆኗን ያወኩት።

እንዲህ ያለው ቀን በቦይፍሬንዴ ተስሜ፣ በፍቅር ተሽሞንሙኜ ውዬ ከቤቱ ስወጣ ሰበር ሰካ እል የለ ? ከአንገቴ ቀና ፣ ከትከሻዬ ነቀል ፣ ከእግሮቼ ፈንጠር እያልኩ እሄድ የለ? ይሄን ግዜ የሚያየኝ ወንድ የለም። ይሄን ግዜ የማታየኝ ሴት የለችም። ጸጉሬን በእጆቼ ወደ ግራ ወደ ቀኝ መታ አድርጌ፣ ደረቴን ነፋ አድርጌ በጎዳና ላይ ሽር ብትን ስል፣ የሚያዩኝ ሥራ ፈትተው፣ ''ዛሬ ደግሞ ምን እናድርግ ? ማንን እንልከፍ....?'' ምናምን ብለው ብቻቸውን የቆሙ ቦዘኔ ወንዶች ብቻ አይደሉም። ከሴት ጋር የቆሙ ፣ ከሴት ጋር የተቀመጡ፣ ከሴት ጋር የሚበሉ ፣ ከሴት ጋር የሚጠጡ፣ ከሴት ጋር የሚራመዱ ወንዶች ሁሉ ፣ አፍጥጠው ያዩኛል።

ከሴት ጋር ስል ዝም ብለው ቱታ ወይ ድርይ ለብሰው፣ ሻሽ ሽብ አድርገው የወጡ ሴቶችን አደለም። ቦርጫም ወይ ብጉራም ፣ ቂጣቸው ከጭናቸው ጋር የተቀላቀለ ዓይነት አይስቤ ሴቶችንም አይደለም።

ቂቅ.....ቋ ብለው የወጡ ፣ በከፍተኛ ሂል ጫማ ላይ የቆሙ ፣ በሂውማን ሄር ያበዱ፣ አንጀታቸው ሙትት፣ ቂጣቸው ውጥት ያሉ ቆንጆ ሴቶችን ማለቴ ነው። እንዲህ ዓይነቷ ሴት ጋር ያሉ ወንዶች ናቸው እኔን ለማየት የሚዞሩት። የሚሰርቁት ዐይኖቻቸውን የሚያንከራትቱት። እህቴን የሚመስሉ ሴቶችን ወገብ አቅፈው የሚሄዱ ወንዶች ናቸው፣ አንገታቸውን አዙረው እኔን ዐይተው ከንፈራቸውን እንደ ምግብ የሚልሱት። ነገሮች ፍፁም ተለዋውጠዋል ። የቁንጅና ጣኦት ፣ በየጎዳናው የምመለክ ጣዖት ሆኛለው። ከእነዛ ውብ ሆነው ከተወለዱ የኤንጅኦ ሴቶች ጋር ምሳ ስወጣ ፣ (በ ''ማን ይበለጥ ያምራል'' አደራደር ቃተኛ ተኮልኩለን ተቀምጠን) ምድረ ሀብታም ወንድ ፣ ምግቡና አጠገቡ ያለች ሴቱን ትቶ አይኑን እኔ ላይ ይሰካል ። እጆቼን ልታጠብ ቋ ቀጭ እያልኩ ስነሳ፣ የሠራውን ጉርሻ አፍርሶ እየተደናበረ ይከተለኛል ።

ሰከርኩ። በመፈለግ፣ በፍላጎት በመታየት፣ ብዛት ብስብስ ብዬ ሰከርኩ።በራስ መተማመኔ በዝቶ በዝቶ፣ ወደ ትዕቢትነት ለመቀየር እስኪደርስ ድረስ በወንዶች የአድናቆት ብዛት ሰከርኩ።

አንዱን ቀን ከቢሮ ሴቶች ጋር እራት ልንበላ አንዱ ቤት ተቀምጠናል። ከገባን ጀምሮ በመጥቀስና በማፍጠጥ መሀል ባለ ሁኔታ የሚያየኝ ፣ ብዙም የማያምር ግን ወንዳ ወንድ ልጅ ፣ ከእኛ ቀጥሎ ያለውን ወንበር ዘሎ ያለው ወንበር ተቀምጧል። አላየውም እልና ዐየዋለሁ። ዐይኖቻችን ሲገናኙ ወሬ እንደያዘ ሰው ፣ ወደ ጓደኞቼ እመለሳለሁ። ደግሞ አሁንም እያየኝ ይሆን ብዬ አስብና ቀና ብዬ ዐየዋለሁ።

አሁንም እያየኝ ነው።

ምን ፈልጎ ነው?

ትቼው ጨዋታውን ቀጠልኩ።

''ስሚ'' አለችኝ ከሰባቱ አንዷ ፣ ደጎረሰችውን ጥብስ ፍርፍር ጨርሳ ሳትውጥ።

''እ....'' አልኩ ፣ ሃሳቤ ከወንዳ ወንዱ ልጅ ሳይላቀቅ። አላየውም...አላየውም.... አላየውም.. ዐየሁት።

እንዳፈጠጠ ነው።

ተሽኮረመምኩና ዐይኖቼን ሰበርኩ።

ሆ!

''....እና ስልኳን ካልሰጠሽኝ ብሎ ወጥሮኛል ...ልስጠው?'' አለችኝ ሕይወት።

ልጁን ሳይ፣ ያለችውን ሁሉ አልሰማሁም።

''ምን?'' አልኳት እያየኋት።

''እንዴ ....አልሰማሽኝም እንዴ?''

''አዎ....ሶሪ....ማነው ስልኳን ያለሽ....?''

እንደገና አየሁት። አየኝና ተነሳ። ቁመቱ መዐት ደልዳላ ነገር ነው።

የት ሊሄድ ነው ?

ሕይወት ታወራለች። በዐይኔ ተከተልኩት።

''እና ልስጠው ?'' አለች ሕይወት።

''ስጪው...'' አልኩና ብድግ አልኩ።

የት ሊሄድ ነው ? ዐየሁት ። ወደ መታጠብያ ቤት ነው የሚሄደው ። ተከተልኩት። ኮራደር ጋር ስደርስቆሞ አገኘሁት።

''እምም...በጣም ታምሪያለሽ....'' አለ።ድምፁ ቁመናውን የሚመጥን ነጎድጓድ ነው።በቆምኩበት ፈገግ አልኩ።

''አመሰግናለው አይባልም እንዴ ?'' አለኝ።

''...ይባላል። አመሰግናለሁ። ሽንት ቤት ልገባ ነው. አንዴ....በቆመበት በቄንጥ እየተራመድኩ ጥዬው ሄድኩ። ዐይኖቹ ቂጤ ላይ ተለጥፈው ይሰሙኛል። ድንገት ዞር ብዬ አየሁት። ልክ ነበርኩ።

'' እጠብቅሻለው....'' አለ ጮክ ብሎ። (አዎ ትጠብቀኛለህ።) ያልመጣ ሽንቴን አልሸና ነገር። ሊፒስቲኬን አስተካክዬ እጆቼን ታጥቤ ወጣሁ። እዛው ቆሟል።

''የምር ጠበቅከኝ አይደል...?'' አልኩ፣ አጠገቡ ስደርስ።

''የእኔ ቆንጆ አንቺ ካልተጠበቅሽ ማን ይጠበቃል ታድያ ?'' (እውነት ነው። እኔ ካልተጠበቅኩ ማን ይጠበቃል?)

ስልኬን ሰጥቼው ወደ ወንበሬ ተመለስኩ።

''ስልክሽ ሲጮህ ነበር'' አሉኝ።ዐየሁት። ቦይፍሬንዴ አራት ግዜ ደውሏል። አንድ ቴክስትም አለኝ። ቴክስቱን ከፈትኩት።

''ቆንጅዬ ናፈቅሽኝ...ማታ አትመጪም?''

ለጀመርያ ጊዜ መልስ ሳልሰጠው ስልኬን አስቀመጥኩና ሕይወትን እያየሁ።

''ማነው ስሙ ስልኬን የምትሰጪው ልጅ?'' አልኳት።

''እንዴ...ያን ሁሉ ስለፈልፍ አትሰሚም ነበር እንዴ...እንዴ ቆይ ደግሞ...ማንነቱን ሳታውቂ ነው ስልኬን ስጪው ያልሽኝ እንዴ?'' አለችኝ በመገረም (ከፈለገኝ ማንነቱ ምን ያደርግልኛል? ''ቆኖጆ ናት ፣ ስልኳን አምጡልኝ፣ ከኔ ጋር እንድትሆን ልልፋ፣ ልድከምላት'' ካለ፣ እኔ ምን ቸገረኝ)

''እ....ጫጫታው አልሰማ ብሎኝ ነው...'' አልኩና ዋሸሁ።

''ቢኒያም ነው ...ያ ዶክመንተሪ የሚሰራልን ልጅ...'' አለች ሕይወት።

ቢኒያም ያሚ! ከማማሩ ብዛት ቢሮ ውስጥ በአባቱ ስም የሚጠራው የለም። ሴቶች ሁሉ ቢኒያም ያሚ ነው የምንለው። ቢኒያም ጣፋጭ...

ቢኒያም ያሚ እኔን ፈለገኝ?...ከዛ ሁሉ ዉበት መሀል እኔን መሠጠኝ?

ቦይፍሬንዴ ደወለ። ዘጋሁበት።

ጭካኔ ሊመስል ይችላል ግን ፣ ''ማንም አይወደኝም ፣ አስቀያሚ ነኝ።'' ብላ ታስራ ትሠቃይ የነበረች የሴትነት ነፍሴን ፣ በአንዲት ቃል ከፈታት ወንድ ጋር በውለታ ብቻ ታስሬ መቆየት አልፈልግም። ይህንን አዲስ ቁንጅና ለዓለም ማካፈል ፣ ለብዙ ወንዶች መበተን አለብኝ። አይመስላችሁም? አስቲ አውሩኝ ከበታች ባለው አድራሻ ሀሳባችሁን ላኩ

🔘አለቀ🔘

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍5🔥1
አትሮኖስ pinned «#ቆንጅዬ : #በሕይወት_እምሻው : #ክፍል_አራት (የመጨረሻ ክፍል) : : ....የእኔ ምስ ግን አንድ ነው ''ቆንጅዬ'' መባል ''የኔ ቆንጆ'' መባል።ከእህትሽ ታምሪያለሽ ብሎኝ አብሬው ያለሁት የመጀመርያ ቦይፍሬንዴ ፣ ለአልጋ ዝግጁ የሚያደርገኝን ቃል ጠንቅቆ ያውቀዋል። ወደ አልጋ ሊያስገባኝ ሲፈልግ ውድ ምሳ፣ ወይ የሻማ እራት አይጋብዘኝም። ወይን አያጠጣኝም። ስጠቶ አሽጎ አያመጣልኝም። ''ቆንጅዬ''…»
#ፍቅፋቂ
:
:
#በሕይወት_እምሻው
:
:
''ዝም ጭጭ! ጩኸት አደለም ብትተነፍሺ በዚህ ጩቤ ነው የምዘለዝልሽ!'' ብሎ አስፈራርቶኝ ነው እዚህ ሜዳ ላይ ያጋደመኝ።

በዚህ ውርጭ፣ በዚህ ጨለማ፣ ሰው ዝር በማይልበት ጥግ፣ ልብሴን ገፎ ቆዳዬን ከአፈር እያነካካ፣ አጥንቴን ከድንጋይ እያማታ የሚያደርገኝን የሚያደርገኝ በጩቤ አስፈራርቶ ነው።

''ሥጋሽን እዘለዝለዋለሁ!'' አለ።

አሁንስ እየዘለዘለኝ አይደለም?

ባልተዘጋጀሁበት፣ ባልጋበዝኩት የወንድ ጩቤው፣ በዚህ በማላውቀው ሰውነቱ....ስጋዬን እየዘለዘለ አይደለም?

አፌን በአንድ እጁ አፍኖ ፣ በሌላው እጁ የተራቆቴ አካላቴን በፍፁም ስግብግብነት ይቧጥጣል።

ስስ ቆዳዬን ባልተከረከሙ ግርድፍና ጨካኝ ጥፍሮቹ ይቀረድዳል፣ እንደ ሎሜ ይጨምቀኛል፣ እንደ ቆሻሻ ልብስ የሸኛል።

ምን አይነት ሰው ነው....?

ከእኔ የስቃይ ጉድጓድ ደስታን የሚቀዳ፣ ስሜን እንኳን ሳያውቀው፣

መልኬን እንኳን ሳያየው ፣ ጓዳ ጎድጓዳዬን ጠርምሶ የገባ፣ ይሄ ምን አይነት ሰው ነው።

አመመኝ።

ለምን አመሸሁ...ባላመሽ ጥሩ ነበር።

ለእማ እንዴት አድርጌ እነግራታለሁ?

አባዬማ ከሰማ ደሙ ከፍ ብሎ እዛው ክልትው ይላል....እማ ''አታምሺ'' ስትለኝ ባላመሽ፤ ላይብረሪ ባልቆይ፣ ይሄ ሁሉ አይመጣም ነበር...

ለመሆኑ...ለመሆኑ...ይህን የሰው እንስሳ....፣ ይሄን ሳልሞት ገሃነም የወሰደኝ ሰው እከሰዋለሁ.?

የት? የሰፈር ፖሊስ ጣብያ...?ፖሊሶቹ ምን ይሉኛል...? ''ለምን በዚህ ሰዐት...?''....ለምን እንዲህ አይነት ልብስ...?...ለምን አልጮኸሽም...? ''ፈልጋ ነው !'' ይሉኝ ይሆን?

የለም አልከስም።

ከሳሽን ተከሳሽ፣ ተበዳይን ጥፋተኛ በሚያደርግ ሕግ ፊት አልቆምም። የተደፋ አንገቴን ይበልጥ ለሚያስደፋኝ አንካሳ ፍትህ፣ እያነከስኩ አልሄድም።

አውልቆ ያልጨረሰው ታይቴ ተረከዜ ጋር ሳይደርስ ተሰንቅሮ ጠፍንጎ ይዞኛል። አፌን ሲከድን አብሮ የያዘው አፍንጭያ መተንፈስ ተከልክሎ ፊቴ ላይ ሲያብጥ ይሰማኛል።

በአይኖቼ ብቻ በእንባ መስታወት ተጋርደው ይሄን ሁሉ የሚሰራኝን ሰው ለማየት ይሞክራሉ። ግን፣ ጨለማው እንዳይ የፈቀደው ጥላውን ብቻ ነው። ሰውነቴን ሰንጥቆ ከገባው ሰውነቱ ጋር ብድግ ምልስ የሚለው የጭንቅላቱ ጥላ ብቻ ይታየኛል።

''ዋ ! እጮሀለው ብትይ!'' አለኝ ደግሞ...የአፍንጫዬን አየር ለማግኘት፣ ከእጆቹ ጥፍነግ ነፃ ለማውጣት ስጥር ተሰምቶት ነው፣ እጁ ሲንሸራተት ትጮሀለች ብሎ ፈርቶ ነው።

ግን እንዲህ ያለ ሰው ፣ ፍርሀትን ያውቃል ? ሌሎቹን የሚያስፈራራ ሰው ይፈራል ? ከገደለ ወድያ የሚፎክር ሰው ሊፈራ ይችላል?

ወይኔ....ወይኔ....ሕመሙ ቀዶኝ የገባው የሰላ ምናምንቴው ውስጤን ይሞርደኛል።

ያመኛል።

ወይኔ እናቴ! ወይኔ...! እንዳላብድ ሌላ ነገር ላስብ

ያቺን ታሪኳ ቡቲክ ያየኋትን ቡትስ ክረምት ሳይገባ በገዘኋት ኖሮ። ውድ ናት፣ ግን በገዛኋት ኖሮ። ቀብድ እንኳን...50 ብር እንኳን ሰጥቻት ብመጣ ጥሩ ነበር። አባዬ ይሞላልኝ ነበር...ከምንም ልብስ ጋር ትሄድ ነበር። በዛ ላይ ትመቻለች። ሱሪ ባደርግ ቀሚስ ባደርግ...ታይት ባደርግ...

ወይኔ ይሄ ታይት ሰንጎ ይዞኛል። የደም ዝውውሬን አቁሞታል። ይሄ ሰውዬ አይበቃውም............? የት ፈልቶ ነው እኔ ላይ ሊሰክን የመጣው.......?

ምን አድርጌ ነው የሕይወቴን ብርሀን አለማስጠንቀቅያ ድርግም ሊያደርግ የመጣው ?
ቴዲስ ምን ይለኛል.....? ቴዲዬ.. ያምነኛል? እንዲህ ሆኜ ነው ብለው ያምነኝ ይሆን...? ይተወኝ ይሆን...?

አፌን እንዳፈነ ተነሳ።

እኔን ያለሁበት ጥሎኝ አፌን እንዳፈነ በርከክ ብሎ ተነሳና ሲሰቀስቁኝ በነበሩ እጆቹ ሱሪውን እየለበሰ፣ ጩቤውን አብለጨለጨና ''እጮሀለው ብትይ ተመልሼ ብትንትንሽን ነው የማጣው!'' ብሎኝ ስ..ል..ብ..አለ፣ ሄደ።

''ተመልሼ እበታትንሻለው !'' ነው ያለው? ምን ቀረኝና ምኔን ተመልሶ ሊመጣና ሊበታትን ነው? በመሰቅሰቅያ መነሳት እስካቸግር መሬት ላይ ተበታትኜ እያየኝ እንዲህ ይለኛል....?

የሰዐት ግምቴ ጠፋ። ግን መሽቶ የነጋ መሰለኝ። እዚያው ውዬ አድሬ የሰው ዘር ያላገኘኝ ፣ ወይ አግኝቶኝ ፤ ''ይህቺማ የሰው ጭላጭ ሆናለች..... የሰው ቅርፊት....ተዋት እዚሁ በስብሳ ትለቅ ...'' ብለው የተውኝ መሰለኝ።

ቤተሰቤም የሆኑኩትን ሰምቶ አናውቃትም ያለ፣ አልሰማንም ያለ መሰለኝ። የተረፈኝን ሰውነቴን፣ ፍቅፋቂዬን ፤ ሰብስቤ ይዤ ቤቴ ስገባ ግን 4:10 ገበር። ይሄ ሁሉ የገሃነም ጉዞ በመደበኛ ሰዐት አቆጣጠር አጭር ነበር።

አዎ.... ሕይወቴና ማንነቴ ለዘላለም የተለወጠው፣ የአንድ እጅ ጣት በማይሞሉ ደቂቃዎች ነው። ቀጫጭን የደም መስመሮች የሸፈናቸው እግሮቼ አላነቃንቅም እያሉኝ ፣ ተነቃንቄ ፣ አላስኬድም እያሉኝ ሄጄ ፣ ቤቴ እንደገባሁ እናቴን ዐየኋት።

ቤቴ፣

ጠዋት ቤቴ ሳለሁ ንፁህ ነበርኩ። ጠዋት ቤቴ ሳለሁ ሙሉ ነበርኩ።

እናቴ፤

ጠዋት ስትሰናበተኝ ንጹህ ነበርኩ። ጠዋት ቁርስ አብልታ ስትሸኘኝ ሙሉ ነበርኩ።

ቆዳዬን እንደ ጃኬት፣ እንደ ቀሚስ አውልቄ ብገባ ተመኘሁ። መርከሴን ፣ ክርፋቴን ደጅ ጥዬው ብገባ ደስ ባለኝ....

እናቴ፣ ''ልጄን.........ልጄን! ምን ሆነሽብኝ ነው ?'' ብላ ልትይዘኝ ስትጠጋ፣ የሳሎኑ መሬት ላይ ስዘረርና ፤

''ጎድዬ መጣሁ እማዬ.....! ጎድዬ መጣሁልሽ....'' ስላት እኩል ሆነ። 😥

🔘አለቀ🔘

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት ምርጦቼ ። 🙏
👍31
አትሮኖስ pinned «#ፍቅፋቂ : : #በሕይወት_እምሻው : : ''ዝም ጭጭ! ጩኸት አደለም ብትተነፍሺ በዚህ ጩቤ ነው የምዘለዝልሽ!'' ብሎ አስፈራርቶኝ ነው እዚህ ሜዳ ላይ ያጋደመኝ። በዚህ ውርጭ፣ በዚህ ጨለማ፣ ሰው ዝር በማይልበት ጥግ፣ ልብሴን ገፎ ቆዳዬን ከአፈር እያነካካ፣ አጥንቴን ከድንጋይ እያማታ የሚያደርገኝን የሚያደርገኝ በጩቤ አስፈራርቶ ነው። ''ሥጋሽን እዘለዝለዋለሁ!'' አለ። አሁንስ እየዘለዘለኝ አይደለም?…»
#ዐልቦ
:
:
#በሕይወት_እምሻው
:
#ክፍል_አንድ
:
''ፍ...ቅ...ር...ተ!''

ስሜ በሴት ሲጠራ ሰማሁና እጆቼን አጎንብሼ ክሰል ከምጎለጉልበት ማዳበርያ ሳላወጣ ቀና አልኩ።

ሴት ናት።

ለሰፈራችን ከልክ በላይ የለበሰች፣ ለተቦዳደሰ ኬር መንገዳችን ከሚመጥነው በላይ ሸላይ ጫማ ያደረገች ፣ ቂ...ቅ ያለች ሴት ናት። ከመስታወት የተሰራ የሚመስለው ባለ ረጅም ስፒል ጫማዋ በሚፈቅድላት ፍጥነት ሚዛኖን ላለመሳት ፣ አንዴ መሬቱን፣ አንዴ እኔን፣ አንዴ ሰፈሩን፣ እያየች አጠገቤ ደረሰች።

አላምንም፣ በጭራሽ አላምንም፣ እስከዳር ናት።

የልጅነት ጓደኛዬ እስከዳር፣ ለዐስራ ስምንት ዐመት ያላየኋት አብሮ አደጌ፣ አሜሪካ ከሄደች ወሬዋን ሰምቼ የማላውቀው፣ የአሁኗ ዲያስፖራ የጥንቷ ባልንጀራዬ እስከዳር ናት።

የአሜሪካ ኑሮ እንደ እጅ ስራ ፎቶ ሞላት፣ አቀላት፣ እንጂ ፣ መሰረቱን በሳተ መልኩ አልተለወጠችም።

እስከዳር ናት!

በዚህ አኳኋኗ ልታቅፈኝ አጠገቤ ሰትደርስ እጆቼ ከሰል ሲቦረቡሩ እንደነበር ታወሰኝ ። ልጄ ያበረሸበት '' ቲቢን በጋራ እንከላከል'' የሚለው ቀበሌ የሰጠኝ ካኔተራዬ ትዝ አለኝ ፣ ጭኔ ላይ የተቦተረፈው ቱታዬ ተከሰተልኝ።

በምን አይነት ቀን ተያዝኩ....? በምን ዓይነት አሳቻ ሰአት ላይ ተገኘሁ ? እግዜሩ ምይ በደልኩት ?ዐስራ ስምንት አመት ጠብቆ ጡቶቻችን ቶሎ እንዲወጡልን የውሃ እናት ካጠባችን የልጅነት ጓደኛዬ፣የዛሬ ዲያስፖራ
- ዘናጭ- ቆንጆ - ብራም - ደስተኛ - ያለፈላት ሴት ፊት በዚህ ሁኔታ ያገናኘኛል? ለእንዲህ ያለ ክፉ አጋጣሚ አሳልፎ ይሰጠኛል?

ሐሳቤ ሳያልቅ ደረሰችብኝ።

''ወይኔ...ጥላሸት በጥላሸት..ምንድን ነው የምታቦኪው ፍቅርዬ? ነይ ቀስ ብለሽ እቀፊኝ...'' አለችኝ።

እያፈርኩ መዳፎቼ ቢጫ እና ነጭ ሸሚዞን እንዳይነካ አንጨፍርሬ ለወጉ አቀፍኳት።

''ኦህ ማይ ጉድነስ...! ፍቅርዬ...ደህና ነሽ...? ምንድን ነው እንዲህ የተጎሳቆልሽው...? ኑሮው ነው ? እኔማ አገኝሻለውም አላልኩ፣ ምንድን ነው ይሄ ሁሉ...? ሰፈራችን የት ደረሰ...? ምን ሆኖ ነው ሁሉ ነገር ብትንትኑ የወጣው...? ሰውስ የት ሄደ...?

የጥያቄ ጎርፍ።

''የቱን ልመልስል....? ብዙ ጥያቄ ነው...ደህና ነሽ ግን...? መቼ መጣሽ?'' አልኩ የተቦተረፈውን ቱታ ሱሪዬን በረጅም አሮጌ እና ቆሻሻ ካኔተራዬ ለመሸፈን እየሞከርኩ፣ ጎላ ድስትን በሚጢጢ ድስት ክዳን እንደመክደን እየሆነብኝ።

''ሦስት ሳምንቴ...ዋ....ው! እኔማ...''አለችኝ! በዐይኖቿ እያጠናችኝ። ሰው እንዴት በዐስራ ስምንት ዓመት ውስጥ ዐይኑ በአንድ መስመር እንኳን አይከበብም....? የኔን ዐይኖች ዐሥራ ስምንት መስመሮች ያጅቧቸዋል ።

ካኔተራዬን ይበልጥ ወደ ታች ጎተትኩት።

''ፍቅርዬ ምንድነው እንዲህ ውድቅድቅ ያልሽው? እንዳገባሽ፤ እንደወለድሽ ሰምቼ ነበር....ምንድን ነው ግን...በጣም እኮ ነው የተጎሳቆልሽው፤ ኑሮሽ ጥሩ አይደለም?'' አለች ዙርያ ገባውን እያየች።

ያላረጀ ዐይኗ ማየት ቢችል፤ ኑሩዬ ጥሩ እንዳልሆነ መልስ አትፈልግም ነበር።

ቡና እና ሻይ ፊት ለፊት ፣ ቀልጦ አገር ያቀልጥ በነበረው መንደር ውስጥ፣ በፍርስራሽ በተከበበ እና በግማሹ የፈረሰ ቤት ውስጥ ነው የምኖረው። ቤቱ በልማት ተገምጧል። ነገ ደሞ ስልቅጥ ተደርጎ ይበላል።

ፈገግ ብዬ ዝም አልኳት።

''እንግባ አይባልም ታድያ?.....''ስትለኝ፣ በከሰል ንክር እጄ እየመራሁ ቤት ወደምለው የግድግዳና የጣርያ ድምር ወሰድኳት።ገባን። እፈረው ቤት ገባን።

ሳሎን ብለን የምናጋንናት ሦስት በሦስት ክፍላችን ውስጥ ፣ ከሞቱት አባትና እናቴ ከወረስኳቸው ፎቶዎች - ሁለቱ አሉ። ሌላው ለወሬ አይበቃምና ይቅርባችሁ።

እኔና ባሌ በርሄ... ቤርዬ ከስድስት ወር ልጃችን ጋር፣ በንፅፅር ሳሎኑን ፈረስ በምታሰኝ፤ በቅርጽ ለቱቦ በምትቀርብ ክፍል ውስጥ እንተኛለን። ትልልቆቹ ልጆቻችን ሰምሃልና ዳንአረል ሳሎን ይተቻሉ።

ይኼወ ነው።

''አይ ካንት ብሊቭ! እስከ ዛሬ እዚህ ቤት እንደምትኖሪ...! ልጆች ሆነን እዚ ሳሎን ጋሽ አባይ እጅ በጆሮ ያስሲያዙን ትዝ ይልሻል?''

አለችኝ።

''እህ...አዎ....ዛሬ ደሞ እኛን ኑሮ እጅ በጆሮ አሲዞናል....ያው የቀበሌ ቤት አይደል...አዲስአባ ዛሬ ለእኛ ዓይነቱ ቦታ የላትም...ስለዚህ የቤተሰብ ቀበሌ ቤት ወርሰን እንኖራለን....እንኖር ነበር ...አሁን እንደምታይው ነው...ሰፈሩ ሁሉ ፈርሶ...ሰው ሁላ...''

''አይ ኖው ! ዋር ዞን እኮ ሚመስለው ! ያልደወልኩለት ሰው የለም እኮ..ግን ሁሉም ሰው ከዚህ ሰፈር እንደወጣ ሰማሁ ለምሳሌ ሀውልት ቦሌ ምን የመሰለ ቤት ሠርታለች አሉኝ። ሠመረና ቢኒ፣ ሁሉም አግብተው ገርጂ አካባቢ መሆናቸውን ሰምቼአለሁ። ፈትለ አሜሪካ ናት...ራሄሌ ስዊድን ነው የምትኖረው፤ ሌላ... ሌላ ኦ...ታሪኳ እንኳን ከዛ መቃብር ከሚመስል ቤት ወጥታ፣ ሰሚት ምን የመሰለ ፓላስ ውስጥ መሰለሽ የምትኖረው...''

ወደ ላይ ሊለኝ ፈለገ።

እሷ አንድ ቦታ ላይ ሩጫ ጀምረን ጥለውኝ የሄዱትን ደርበውኝ የሮጡትን፣ የሰፈራችንን ልጆች የዛሬ ኑሮ ስትነግረኝ፣ ወደ ላይ ሊለኝ ፈለገ። ስሜቴ የገባት አልመሰለኝም።ይሄ አሜሪካ የስሜት ማንበብያ በቀዶ ጥገና ያስወጣል እንዴ?

ቀጠለች፣

''...ግን ፍቅር...ምን ሆነሽ ነው ያ ሁሉ ሰው ሲወጣ አንቺ ብቻ እኮ የቀረሽው...ማለቴ ኦልሞስት ትዊንቲ ይርስ..ዛት ኢዝ ኤ ሎንግ ታይም ኖት ቼንጅ...መቼም ህልምሽ ይሄ አይመስለኝም..ምን ሆንሽ...''

''ለስላሳ ነገር ላምጣልሽ?'' አልኳት ፍንጥር ብዬ ተነስቼ።

''ለስላሳ ላምጣልሽ..ምን ይሁንልሽ...?''

''ኦ ኖ...ለስላሳ አልጠጣም....ዳይት ላይ ነኝ... አታይኝም ተዝረጥርጬ...'' አለችኝ። ልብሷ ብቻ ሳይሆን ቆዳዋ እንደጠበባት ያስተዋልኩት ገና አሁን ነው።

''አሜሪካ ያወፍራል መሰለኝ....''

''አዎ ምግቡ...ዝም ብለን በመኪና ስለምንዞር፣ በዚያ ላይ....በነገርሽ ላይ...መኪና ያቆምኩት በፊት ጠጅ ቤት የነበረበት ቦታ ነው። ሴፍ ነው አይደል..? የሆኑ ልጆች እንደ ጉድ ሲያዩኝ ነበር..''

ሣቅ አልኩና ፣ ''ሰላም ነው...ምንም አይሆንም እና ምንም አትበይም...?''ባዶ ቤት አጉል ሰአት መጣሽ...'' አልኳት።

''ኖ ፣ ዛት ኢዝ ሶ ኦኬ ይልቅ...ማታ እንውጣ... አንቺም ፈታ በይ...ቀና ቀና ብሏል ዘፋኙ...'' አለች ብድግ ብላ።

''ማን ነው እሱ ደግሞ?''

''አብርሃም ወልዴ ነው ማነው?...አይ ላቭ ዛት ሶንግ ! ''

''እሺ ፣ ግን...ባሌን ልንገረው መጀመርያ...'' አልኩ እያቅማማው። የማስበው ልለብሰው ስለምችለው ልብስ ነው። የማስበው ስለተንጨበረረው ጸጉሬ ነው። ታኮዋ ስለላላችው፣ ብቸኛዋ ''የውጪ ጫማዬ ነው።

''ኦ ማይ ጋድ! ዋት ኢዝ ዚስ...ናይንቲን ሰርቲስ..? የሱን ፍቃድ መጠየቅ አለብሽ እንዴ..?

''እንዴ አስኩ..ትዳር እኮ ነው..በዛ ላይ ህፃን ልጅ አለኝ..መያዝ አለበት''

''ቢሆንም..ኤኒ ዌይ...አስካሁን አለመጠየቄ ይገርማል..ማነው ስሙ ባልሽ...?

''በርሄ...በርሄ ይባላል።''

ልክ እንዲህ ስላት ፣ እጆቿን እያማታች፣ በሹል ጫማዋ የተቦረቦረ ሊሾ መሬቴን እየደቃች፣ ''ኖ ዌይ...! '' አለች።

''ምነው...አታውቂም ነበር...? ቤሪን እንዳገባሁ...'' አልኳት ፊቷን እየሰለልኩ። የዋሸችኝ መሰለኝ...

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት።
👍31
አትሮኖስ pinned «#ዐልቦ : : #በሕይወት_እምሻው : #ክፍል_አንድ : ''ፍ...ቅ...ር...ተ!'' ስሜ በሴት ሲጠራ ሰማሁና እጆቼን አጎንብሼ ክሰል ከምጎለጉልበት ማዳበርያ ሳላወጣ ቀና አልኩ። ሴት ናት። ለሰፈራችን ከልክ በላይ የለበሰች፣ ለተቦዳደሰ ኬር መንገዳችን ከሚመጥነው በላይ ሸላይ ጫማ ያደረገች ፣ ቂ...ቅ ያለች ሴት ናት። ከመስታወት የተሰራ የሚመስለው ባለ ረጅም ስፒል ጫማዋ በሚፈቅድላት ፍጥነት ሚዛኖን…»
#ዐልቦ
:
:
#በሕይወት_እምሻው
:
#ክፍል_ሁለት
:
''በጭራሽ...! ታድያ የሰፈር ልጅ...ያውም የእቃ'ቃ ባልሽን አግብተሽ ነዋ እዚህ ተቀብረሽ የቀረሽው....! ወይኔ በጣም ይገርማል..በጣም..''

ሳትጨርስ ልጄ አለቀሰ።

በሕይወቴ ፣ ''እሰይ ልጄ አለቀሰ'' የሚያስብለኝ አጋጣሚ ይፈጠራል ብዬ አስቤም አላውቅ፣ ግን ተፈጠረ። በቆመችበት ትችያት፤ አንስቼ ላባብለው ወደ ''መኝታ ክፍሌ'' ሮጥኩ።

=========-------===========
''ቤቷ ብቻ ስንት ካሬ እንደሆነ ታውቃለህ...? ሁለት መቶ ሃምሳ! ሁለት መቶ ሀምሳ ካሬ! አስበው..... ከዚህ እስከ ደብረወርቅ ህንፃ ማለት ነው.... ቤቷ፣ ከእኛ ቤት እስከ ደብረወረቅ ሕንፃ ነው....! በዛ ላይ እቃዎቿ....ሶፋ ብትል....የእኛን አልጋ ሦስት እጥፍ የሚሆን ሶፋ...ፍላት ስክሪን ቲቪ... የውጭ በር የሚያክል ፍላት ስክሪን ቲቪ አላት.... ምንጣፉ.... እዚያ ሁሌ የማየው..... ሁሌ የምመኘው ሁሌ ግዛልኝ የምልህ ኮምፎርት ትዝ ይልሀል....ያ ሳሪስ ያለው ቤት....እሱን ነው የሚመስለው.... እሱን ነው የሚረግጡት.. እ...''

እየተስገበገብኩ ነው የማወራለት - ለቤሪ። እስኩ ጋር አምሽቼ ምምጣቴ ነው። የአሜሪካው ቤቷን በስልክ ላይ፣ ፎቶና ቪዲዮ አይቼ መምጣቴ ነው። በቢራና በቅናት ተሞልቻለሁ።

''ፍቅር....'' አለኝ ቤሪ፤

''ወዬ...'' ገና አልጨረስኩልህም እኮ.....መኝታ ቤቷ ባርኮን ይሙት....''

''በልጅሽ አትማይ! ከመቼህ ወዲህ ነው በልጃችን የምትምይው?''

''አይደለም እኮ...''

''ኡፍ...በቃኝ ስለሷ ቤት መስማት አንቺም ይበቃሻል....መሽቷል፤ እንተኛ....ልጄንም እንዳትቀሰቀሽው....'' አኮረፈኝ መሰለኝ።

''ለምን ታኮርፈኛለህ?'' አልኩት ወደ መኝታ ስንሄድ እጁን ጎትቼ አስቁሜው። ለብታዬ ወደ ሞቅታ እያደገ መሰለኝ።

''አላኮረፍኩም ፍቅር ግን ሰለቸኝ...እኛ ብዙ የምናስበው ነገር አለ ልጆች አይደለንም ልጆች አሉን....''

''ጥሩ ነገር...ጥሩ ነገር ማውራት ይሰለቻል....? እኛ ባይኖረን ሌላው ያለውን ማውራት ይበዛብናል?'' አልኩት አልጋው ውስጥ ሲገባ ቆሜ እያየሁት።

''ምን ሆነሻል....? ሌላ ሰው ሆንሽብኝ... አራት ቢራና ነገር አጠጥታ ላከችብኝ ሚስቴን...ቀንተሻል...? በድሮ ጓደኛሽ ኑሮ ቀናሽ?''

ቤሪ እንደዲህ ነው። ዙርያ ጥምጥም አያቅም ፣ ነገር ማሰላሰል አያውቅም። መሸፋፈን፣ መጀቧበን፣ በስውር ማውራት አይችልበትም።

በዚህ እወደው ነበር ፣ ደስ ይለኝ ነበር ፣ ዛሬ ግን አበሳጨኝ።

''ብቀና ሀጥያት ነው...?'' አልኩት ድምፄን ከፍ አድርጌ።

''አትጩኺ'' ባርኮን ይነሳል፣ ደግሞ አዎ...ቅናት ሀጥያት ነው''

''ባክህ አትመፃደቅብኝ....ጥሩ ነገር መመኘት ሀጥያት አይደለም...እኔስ ሰው አይደለሁም...? ጥሩ ነገር አያምረኝም...አይገባኝም...? ዘላለም እንዲህ ያለ ጉሮኖ ውስጥ እየኖርኩ፤ እህል ቅጠል የማይል ወጥ ቀቅዬ እንድበላ፣ የልጅ ቅርሻት ስጠርግ እንድኖር የተፈረደብኝ ይመስልሀል..? ደህና ነገር አይወድልኝም...?'' አልኩት። የራሴ የምሬት ድምፅ ይሆን ያለመድኩት ቢራ አፌን ሲመረኝ ይሰማኛል።

ቤሪ ቅስሙ ሲሰበር ዐየሁት፣ በሚታይ ሁኔታ ቅስሙ ስብር አለ።

አንደሚያስብ ሰው ትንሽ ዝም አለና ፣ አለና ፣ ይሄ ሁሉ የታየሽ ዛሬ እሷ ስትመጣ ነው...? የሌለሽን ነገር እስኪ እዪው ብላ ፊትሽ ላይ ስትወረውረው ነው ኑሮሽ ያስጠላሽ? ፍቅር ሰክረሻል...የምትይውን አታቂም እንተኛ...ነገ እናወራለን...'' ብሎ እጁን ዘረጋልኝ። ዝም ብዬ አየሁት።

''ፍቅር ነይ አልጋ ውስጥ ግቢ...የኔ ሰካራም አቅፌ አስተኛሻለሁ... ነይ...'' አለኝ የተዘረጋ እጁን ሳያጥፍ።

አልጋውን አየሁት፣ ሲያስጠላ። ክፍሉን ዐየሁት፣ ሲቀፍ።

የተቦረቦረ ግድግዳችንን፣ የተበሳሳ ጣርያችንን፣ ምንጣፍ አልባ ወለላችንን፣ ቁምሳጥን የለሽ ርካሽ ልብሶቻችንን፣ መስኮት አልባ፣ የሚሰነፍጥና የሚያፍን ሕይወታችንን ዐየሁት። ሁሉንም ተጠየፍኩት።

ባሌን አየሁት፣ ደጅ ድንጋይ ላይ ቁጢጥ ብሎ፣ በግራው ሚጢጢ መስታዎት ይዞ፣ በቀኝ እጁ ራሱ የሚከረክመውን ጢሙንና ፀጉሩን ዐየሁት። በላብ የሚያበራ ጎስቋላ ፊቱን ተመለከትኩት፣ የለበሰውን የወንድሙን ውራጅ ፒጃማ ዐየሁት።

የምወደው ቤሪንም ከቤቱና ከቅራቅንቦዬ ጋር ደምሬ ተጠየፍኩት።

''ነይ እንጂ የኔ ሰካራም...ነይ!'' አለኝና ገብቶ ከነበረበት አልጋ ተነስቶ ወደ እኔ መጣ። ልሄድ ፈለኩ ግን እግሬ አልሄድ አለ ።እግሮቼ ዝናብ ከመታው ግንድ ከበዱኝ።የሞት ሽረቴን ልጠጋው ስሞክርና ''ቤቢ ፊያት'' የምታክል አይጥ በባዶ ቀኝ እግሬ ላይ ስትሄድ አንድ ሆነ። ከተበሳሳው ጣርያችን በላይ ጮኽኩ።

''ምነው ምን ሆንሽ....?'' ብሎ ተስፈንጥሮ አቀፈኝ። ከእቅፉ ለማምለጥ እየሞከርኩ፣ ኤጭ አሁንስ! ወይኔ አሁንስ...ኤጭ...!'' እያልኩ መጮኼን ቀጠልኩ።

''ምንድን ነው ፍቅ...ር...? ምንም አላየሁም እኔ...ሳትተኚ ቅዠት ጀመርሽ እንዴ!'' አለኝ ሊይዘኝ እየሞከረ።

''ከዚህ በላይ ቅዠት አለ? ቅዠት ከዚህ ኑሮ በላይ አለ የማይባንኑበት ቅዠት!''

''ምንድን ነው የምታወሪው...?

''እግሬ ላይ የሄደችውን ግብዲያ አይጥ አላየሁም ለማለት ነው?'' አልኩት የረገበ አልጋችን ላይ ብቻዬን እየወጣሁ። ልጄን ለማባበል ነው የሄድኩት። ልጄ በጩኽቴ ተቀስቅሶ ማልቀስ ጀምሮል።

''እና አይጥ አዲስ ነገር ነው እዚህ ቤት? ስም ሁሉ አውጥተንላቸው የለ...? ማናት የሄደችብሽ ዘርትሁን ወይስ ባንቺ ይሩጉ....? እያለ መሳቅ ጀመረ።

እጄ ውስጥ ያለው ልጄ ባይሆን ወርውሬ ጥርሱን ብሰባብረው ደስ ይለኝ ነበር።

''በርሄ አያስቅም ፣ በዚህ አትሳቅ...አባዬ ይሙት አታናደኝ''
''በርሄ ደሞ ማነው...? ሃ ሃ ሃ...'' አረ ለመሆኑ ከመቼ ወዲህ ነው በአይጦቻችን መሳቅ ያቆምነው?''

'' ከዛሬ ጀምሮ!'' አልኩት የልጄን ለቅሶ ለማስቆም ከግራ ወደቀኝ ከቀኝ ወደ ግራ እየወዘወዝኩት።

''ለምን..?''

''ስለመረረኝ፣ ስለታከተኝ፣ ከአይጥ ጋር መኖር ስለታከተኝ...አንተም ሊመርህ ይገባል። ከአይጥ ጋር መኖር የሚፈልገው ድመት ብቻ ነው።ድመትም ቀለቡ ስለሆኑ ብቻ...እኔ ምኔ ድመት ይመስላል?''

''ወይ ጉዴ...እኮ ዛሬ ምን ተገኝቶ ነው፣ እንዲህ ባንዴ የተለዋወጥሽው?'' አለ በስጨት ብሎ።

ዝም አልኩት።

ዛሬ ምን ተገኝቶ ነው፣ አስቤዛ እየተሰፈረላቸው የኖሩት አብሮ አደጎቼ አይጦች እንዲህ ያማረሩኝ ...?ዛሬ ምን ተገኝቶ ነው፣ የምወደውና እና የሚወደኝ ባሌ እንዲህ ቱግ ቱግ የሚያሰኘኝ.? ዛሬ ምን ተገኝቶ ነው፣ የማርፍበት ቤት እረፍት የነሳኝ....?

''አስከዳርይን ስታገኚ ሕይወትሽ አስጠላሽ...? እኛ አስጠላንሽ አይደል ፍቅር...? እኛ አስጠላንሽ አይደል ፍቅር.....?'' አለ በተሰበረ ድምፅ ወደ እኔ እየመጣ።

ዝም አልኩት።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍42
አትሮኖስ pinned «#ዐልቦ : : #በሕይወት_እምሻው : #ክፍል_ሁለት : ''በጭራሽ...! ታድያ የሰፈር ልጅ...ያውም የእቃ'ቃ ባልሽን አግብተሽ ነዋ እዚህ ተቀብረሽ የቀረሽው....! ወይኔ በጣም ይገርማል..በጣም..'' ሳትጨርስ ልጄ አለቀሰ። በሕይወቴ ፣ ''እሰይ ልጄ አለቀሰ'' የሚያስብለኝ አጋጣሚ ይፈጠራል ብዬ አስቤም አላውቅ፣ ግን ተፈጠረ። በቆመችበት ትችያት፤ አንስቼ ላባብለው ወደ ''መኝታ ክፍሌ'' …»
#ዐልቦ
:
:
#በሕይወት_እምሻው
:
#ክፍል_ሦስት (የመጨረሻ ክፍል)
:
:
....''ልጄን ስጪኝ...! እንዲህ ሆነሽ ማልቀስ አያቆምም'' አለና ባርኮንን ተቀበለኝ፣ ሳላንገራግር አቀበልኩት። ቤሪ ልጃችንን በለመድነው ወጉ፣ በእሹሩሩ ዜና ለማስተኛት ሲያባብል፣ በለመደው ወጉ ጥሩ አባት ሲሆን እያየሁ እራሴን እንዲህ አልኩት።

'' እውነት ግን ምን ሆኜ ነው?''
===========================

በሱ ቀሚስ ብታስነጥሺ የጡቶችሽ ጫፍ ሳይታዩ አይቀሩም አለኝ ቤሪ፣ ከእስኩ ጋር ላለኝ የማታ ቀጠሮ ስበጃጅ።

ትላናንት ማታ ከተፈጠረው ነገር በኋላ ፣ ለቀልድ የሚሆን ፍቅር ስለቀረው አንጀቴን በላው። ፊቴን ባልለመደው አኳኋኑ ስቀባና ሳጠፋ፣ ሥሰራና ሳፈርስ፣ አዲስ ሰው ስሆን ፤ እያየኝ ለመሳቅ መሞከሩን ሳይ አንጀቴ ተንሰፈሰፈ። ዞር ብዬ አየሁት።

ባርኮንን እያጫወተ ሳይሰርቅ ያየኛል።

''በጣም ጠበበ እንዴ....''? ሊያይወም እሷ ድሮ ገዝታው ሳትለብስ የቀረችውንእኮ ነው የሰጠችኝ
.. አሁንማ ተቀዶም ሌላ ቀሚስ ገብቶበትምአይሆናት'' አልኩት፣ እኔም ሳቅ ለመፍጠር እየሞከርኩ።

''ቢጠብም ያምርቦሻል...የኔ ሚስት እንኳን ሦስት የወለድሽ በልተሽ የምታድሪ አትመስይም እኮ....! አለኝ፣ ልጁን እንደያዘ እየተጠጋኝ።

ማታ እንድያ ጥንብ እርኩሱን አውጥቼው ጠዋት ቅዱስ የሚሆን ይሄ ሰው ከምንድን ነው የተሰራው ..? ለምንስ ነው ለኔ የተሰጠኝ..? ጸጸት ሹክ አለኝ።

''ቂጣምዬ....'' አለኝ ፣ ባርኮንን ባልያዘው እጁ ቂጤን ቸብ እያደረገኝ።

''አንተ እረፋ...''

''ምን አገባሽ በኔ ቂጥ....''

''ሂድ ወደዛ...የኔ ነው...''

በሚጢጢ ቤታችን ውስጥ እንኳን መሮጥ ፈጠን ብዬ ብራመድ ከግድግዳ እጋጫለሁ እንጂ፣ ሮጬ የህንድ ፊልም ነገር ብንሰራ ደስ ይለኝ ነበር። ይሄንን ጊዜ ልሰጠው ፣ ይሄንን ጨዋታ ልሸልመው ብችል፣ ደስ ይለኝ ነበር።

''እረፍ እየጠበቀችኝ ነው አሁን ቶሎ ልሂድ..'' ስለው ፣ ወደ አሮጌው ፎቴ ተመለስና ዝርፍጥ አለ።

''ቤሪ...?'' አልኩት ሊፒስቲኬን መልሼ እያስተካከልኩ። ከንፈሬ ወሰኑ አይታወቅም። አገጬን እየተቀባሁ ተቸገርኩ።

''ወይ ፍቅር..''

''እንዲህ ብዘንጥ ደስ አይልክም ሁሌ...? ማለቴ እንዲህ ቁልትልት ብል..ዝንጥንጥ...?''

''አንችን ደስ ይልሻል ፍቅር...? ያ ሰባራ ድምፁ ተመልሶ መጣ። ''መዘነጥ ማን ይጠላል...? ዞር ብዬ ወገቤን ያዝኩና መለስኩለት።
''ለኔ ጆንያም ብትለብሺ ውብ ነሽ..ደስ ካለሽ ግን ዘንጪ...''

ቮድካ በዚህ መጠን ጠጥቼ አላውቅም። ነገሮች ሁሉ ይበወዝብኝ ጀመር። አስኩ አራት ከንፈር፣ ስድስት ጆሮና አራት ዐይን ያላት ይመስለኝ ጀመር።

የጎደለ ብርጭቆዬን ልትሞለው ስትል በደመነፍስ፣ አንቺ በቤሪ ሞት...በቃኝ...'' አልኩኝ፣ የብርጭቆዬን አፍ በእጄ ለመክደን እየሞከርኩ።እኔ ይህን እያልኩ፣ ክዳን ያደረኩትን እጄ ላይ ቮድካውን ስትቀዳ፣ ነገር አለሙን ትተን እንደ ቂል መሳቅ ጀመርን።

''አንቺ እረፊ....ሰካራም!'' እላታለሁ፣ ትስቃለች።

''ወይኔ ቤሪ ይሙት...ቤሪ ይሙት...በቃኝ አልኩሽ እኮ!'' አልኩኝ እየሳቅኩ።

እጄ ላይ መቅዳቷን ሳታቆም አሁንም ትስቃለች። የሞት ሞቴን ጠርሙሱን ተቀበልኳትና ሶፋው ላይ በጀርባዬ ተጋለልኩ። ስገባ በብርሀን ተሞልቶ የነበረው ክፍል ጨላለመብኝ። አይኖቼን አሸሁ። አሁንም እንደጨላለመብኝ ነው።

''ውሃ...ውሃ ስጪኝ አስክዬ...'' አልኳት በተንጋለልኩበት።

''ምን ሆንሽ....?'' አለች፣ ውፍረቷ እና ጫማ የጨመረው ቁመቷ ተኝተው ሲያዩት ያስፈራል። ቀና ለማለት ሞከርኩ።

''ተቃጠልኩ አስኩ...ቅጥል አደረገኝ...''

''ጎሽ...የሚያቃጥልሽን አቃጠለው ማለት ነው አሁን...ሠርቷል ማለት ነው...!'' አለችና መውደቅን እንደ ፈራ ሰው እየተጠነቀቀች አጠገቤ ቁጭ አለች።

''አረ እኔ በዚህ ሁሉ የሚቃጠል ነገር የለኝም!'' አልኳት፣ አልታዘዝ ያለኝ አንገቴን አዙሬ ላያት እየሞከርኩ።

''እስኪ ማይልኝ...!'' አለችኝ እግሯን ወደ እጆቼ እየላከች፣ ክትክት ብለን ሳቅን።

''ቤሪ ይሙት..!'' አልኳሏት አየሩን በእጄ በመሀላ እየመታው።

''ወይ ይሄ ቤሪ ይሙት..ከእነረ እኮ በባሌ ብምል.'' አለችኝ እየሳቀች፤

''እ...'' አልኳት

''ይሙት ካሉክ ምኞት ነው እንጂ መሀላ አይሆንም''

''ሃ ሃ አስኩ ቀልደኛ ነሽ....''

''ቀልዴን አይደለም..." ክልትው ይበል!''

ሣቋ በዚህ ፍጥነት የት ገባ?

''አንቺ በቮድካ የሚቃጠል የለኝም አልሽ አይደል እኔ ግን አለኝ...ውቅያኖስ የሚያክል ቮድካ አቃጥሎ የማይጨርሰው ነገር ውስጤ አለ ፍቅር...ተቃጠልኩልሽ....''

በድንገት እንደሚያቅፍም እንደሚደግፍም ሰው፣ በተቀመጥኩበት አፍናኝ ታለቅስ ጀመር። ወዝገብ አለብኝ።

''እንዴ...! ምን ሆንሽ ድንገት...?'' አልኳት፣ ሶፋው ላይ ተመቻችቼ ላመቻቻት እየሞከርኩ።ቆዳ ነኝ የሚለው ጥቁር ፕላስቲክ ልብሱ፣ መልሶ መላልሶ ያንሸራትታል።

''ኑሮ አቃጠለኝ...ተቃ...ጠልኩ አልኩሽ በቃ...ጓደኛዬ ሕይወቴ አቃጠለኝ....''

ለቅሶዋ ባሰ፣ ሁሉ ነገር ድንገት ሆነብኝ። እንባዋ ቮድካዬን የመጠጠው ይመስል ስካሬ ሲበን ተሰማኝ። ቀና አልኩ።

''ምን ሆንሽ..?'' ምን ጎደለብሽ....? ሰክረሽ ነው.. የምትቀባጥሪው...? '' ምን አለኝ...? ምንም የለኝም እኮ ጓደኛዬ...ባዶ...ባዶ ነኝ እኮ እኔ... ኔፓ ...ዜ...ሮ...ዜ....ሮ....!''

ለሀጯ እየትዘረበረበ፤ ንፍጧ እየትዘረከረከ፤ እምባዋ እየወረደ፤ ሳያት፣ ቮድካው ሳይሆን እሷ እያወራች መሆኑ ገባኝ።

''ምን የለሽም....? ቤት መኪና... ልጅ.... ባልሽ.. እኔ ምን አለኝ...? ሩዬን እያየሽው ባንቺ ኑሮ ትማረርያለሽ ? ቤቴን አይተሽው ምንም የለኝም ትያለሽ..እኔኮ መንግስጥ የሰጠኝ ኮንደሚኒየም ቤት አድሼ መግባት አቅቶኝ፣ እዛ ጉሮኖ ውስጥ የምኖር ሰው ነኝ...እንቺ ምን የለሽም?'' አልኳት እያቀፍኳትእያቀፍኳት፤ እንደ ህፃን ልጅ እያናፈጥኳት፣ እንደ ባርኮን እያባበልኳት።

'' ባሌ...ቴዲ...ባሌ እኮ ጥሎኝ ከሄደ ዓመት ሞላው ፍቅር....ጥሎኝ ሄደ.....ትቶኝ ሄደ.....''

ደነገጥኩ።

''እንዴ....መቼ....?''

''አመት አልኩሽ አይደል....?''

''አይደለም...እንዴት ማለቴ ነው...? መቼ ሳይሆን እንዴት....? ደንበርበር አልኩች።

እስካሁን ያልነበረኝ እንግዳ መረጃ ነው። ያን ሁሉ የምቾት ክምሯን በፎቶ ላይ፣ በቪዲዬ ስመለከት ፣ ''ባልሽ የታለ?'' ብዬም አልጠየቅኩ፣ እሷም አልነገረችኝ።

''ይሄውልሽ ....'' አለች፣ እየተንፏቀቀች ከተጋደመጅበት የሆቴሏ ሶፋ እየተነሳች ፣ ''ይሄውልሽ...ጢቢጢቢ ሲጫወትብኝ ኖሮ... ጥሎኝ ሄደ...''

''እ...ማለት....ምን ብሎ?''

''ከአንዷ ደጋን እግር ጋር ፍቅር ያዘኝ ብሎ'' ዝም አልኩ።

ለእንዲህ ያለው ነገር ምን ተብሎ ይመስላል? ጓደኛዬ፣ ''ባሌ ጢቢጢቢ ተጫወተብኝ፣ ሌላ ሴት ወዶ ጥሎኝ ሄደ....ተቃጠልኩ!'' ብላ ስትል ፣ ምን ማለት ነው ያለብኝ?

''አይዞሽ አስኩዬ....''

ለማለት የቻልኩት ይህችን ብቻ ነበር።

''አይዞሽ አሰኩዬ...'' ደገምኩት

''አውሬ ነበር፣ የሰው አውሬ።እኔ ጫካ ሆኜለት ችዬው ኖርኩ እንጂ፣ አውሬ ነበር...እላዬ ላይ ሴት ይዞ ይመጣል፣ ልጁን ይክዳል ፣ ሌላውን ተይው ፍቅር....እርጉዝ ሆኜ...እርጉዝ ሆኜ እንኳን ፍቅር..'' ለቅሶ አሸነፋትና መናገር አቆመች።

የምላት ነገር አጣሁ።
👍51👎1
ቤሪን አሰብኩት። ቤሪ...ሐሳቤ ወሬዋን ስትቀጥል ተቆረጠ።

''እርጉዝ ሆኜ.... እሱ እየነዳ....አብሬው ሆኜ.... ትንሽ ካስቆጣሁት...ኢን ዘሚድል ኦፍ ኖ ዌር...ገፍትሮ ያስወርደኛል...ዋን ታይም....አይ ወዝ ሲክስ መንዝ ፕሬግናንት ዊዝ ብሩህዬ... ጣቱን ሳየው....ቀለበቱን ሳጣው...የት ሄደ? ሰለው...ሃይዊይ መሀል ካልወረድሽ ብሎኝ...በመከራ ለምኜ ነው የተረፍኩት ፍቅር... እንዲህ አይነት ሰው ነው።''

ለቅሶዋ ያባባል።

ከአምስት ቀን በፊት ሰበር ሰካ እያለች ሰፈሬ የመጣችው አስኩበዚህ እምባ ብዛት የሟሟች መሰለኝ። ምስኪን፣ እንስ፣ ጎምላላዋ ጓደኛዬ አነሰችብኝ።

ቤሪን ደግሜ አሰብኩት። ባርኮንን እርጉዝ ሆኜ ግማሽ ባልዲ ውሃ ተሸክሜ ስገባ አግኝቶኝ እብደት ቀረሽ ንዴት...ያገኛትን ሳንቲም አገጫጭቶ ስጋ ገዝቶልኝ መምጣቱ...ሁለት እንቁላል ብዙ አስመስሎ መጥበሱ..ሆዴን ሌት ተቀን እየዳበሰ ግንባሬን አሳሳሙ...

ቤሪ.....

''አንዴ ምን እንዳለኝ ታውቂያለሽ...? ስትለኝ ወደ ሆቴል ክፍሏ ተመለስኩ።

''ምን አለሽ ሆዴ...?''

''አንቺን እኮ ችዬሽ እኖራለሁ እንጂ ወድጄሽ አላውቅም....አይ ቶሌሬት ዩ....ሰው እንደዛ ይባላል ፍቅር....? የልጁን እናት እንዲህ የሚል ሰው አለ....? እንዲህ አይነት ባል አለ...? ንገሪኝ እንጂ....ያንቺ ባል እንደዚህ ነው?''


እያባበልኳት ባሌን አሰብኩት። የኔ ባል ስሜን ባጠራሩ እንደሚወደኝ ይነግረኛል።ልጆቻችን በአያያዙ ፍቅሩን ይገልፅልኛል። የኔ ባል፣ ትሪ የሚያሳይ እንጀራችንንሳይሰስት እያጎረሰ አፍ አውጥቶ፣ ''አፈቅርሻለው'' ይለኛል። የኔ ባል ከሰል ሳቀጣጥል ስጨናበስ ስንጥር ለቃቅሞ አምጥቶ ሲያግዘኝ እንደሚያመልከኝ ይነግረኛል።

የኔ ባል....

አስኩ ዞር አለችና ዐይን፣ ዐይኔን እያየች፤ '' ባንቺ እቀናለው ፍቅር... በትዳርሽ...በበርሄ... አውቃለሁ ቅናት ኋጥያት ነው ግን....ቀናሁ...በባልሽ ቀናሁ!'' አለችኝ።እምባዬ እየታገለኝ አቀፍኳት።

ሐዘኗን ለመጋራት አልነበረም ለቅሶዬ። የሚያስቀና ባሌን ዕይው ብላ ስላሳየችኝ፣ በግድግዳ እና በጣርያ ፣ በሶፋና ቴሌቪዥን፣ በምንጣፍ እና በአልጋ፣ ጋርጄው የነበረውን፣ የሚቀናበት ባሌን ዕይው ብላ ስላሳየችኝ በራሴ አዘኜ ስለነበር ነው ለቅሶዬ፣ያለኝን ለማወቅ ሰው ስላስፈለገኝ ነው እምባዬ ፣ ጥብቅ አድርጌ አቀፍኳት።

ዐይኔን የገለጠችልኝን የልጅነት ጓዴን ፣ ጭምቅ አድርጌ አቀፍኳት።

በበነጋው፣ ስካራችንም ነገራችንም በርዶ፣ ወደ ቤቴ ሸኝታኝ ስትሰናበተኝ፣አጥብቄ ሳምኳት።ከሚኪናዋ ዘርጄ ቤት ገባሁ። ከመግባቴ፣ እንደ አዲስ በተገለጠ ዐይኔ፣ በፈራረሰ ሰፈርና ቤት ውስጥ ፀንቶ የቆመውን ትዳሬን፣ ፍቅሬን፣ባሌን ሳየው፣ ፍፁም በደስታ ተሞለሁ።

💫አለቀ💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍31
አትሮኖስ pinned «#ዐልቦ : : #በሕይወት_እምሻው : #ክፍል_ሦስት (የመጨረሻ ክፍል) : : ....''ልጄን ስጪኝ...! እንዲህ ሆነሽ ማልቀስ አያቆምም'' አለና ባርኮንን ተቀበለኝ፣ ሳላንገራግር አቀበልኩት። ቤሪ ልጃችንን በለመድነው ወጉ፣ በእሹሩሩ ዜና ለማስተኛት ሲያባብል፣ በለመደው ወጉ ጥሩ አባት ሲሆን እያየሁ እራሴን እንዲህ አልኩት። '' እውነት ግን ምን ሆኜ ነው?'' ===========================…»
#አለማምጂኝ
:
በጨበጥኩት ብዕር
ውበትሽን ልገልጠው ቃላት ባማርጥም፤
ቤት መምቻ ቸግሮኝ
አጥር ላይ ቆሚያለሁ ስላንቺ ሳልገጥም፤
:
#አለማምጂኝ
:
ወይ አልገጠምኩልሽ
ቤቱን እየመታሁ፤
ወይ አልተመለስኩኝ
ቅኔዋን ውበቴን አንቺን እየፈታሁ፤
ልፈታሽ ብጥርም
ማሠሪያሽ ቸገረ፤
ቀን በቀን እያደር
ውበትሽ ጨመረ፤
:
እንዴት ላ'ርገው?..
:
#አለማምጂኝ


እስቲ ነይ ወደኔ
ውብ ገላሽን አምጪው፤
የማይገጥም ጣቴን
ብዕር አስጨብጪው፤
ቅኔሽን ስፈታ አግዢኝ ነይ ፍቺ፤
አጥሩ ላይ ስደርስ
ደርሰሽ ቤቱን ምቺ፤
ተባብረን እንፃፈው
በልብ የታመቀ ያልተፃፈ እውነት፤
ይህ ነው ግጥም ማለት፤

🔘ልዑል ሀይሌ🔘
#አይ_ሽብሬ
:
:
:
አግብቼ ከእናት ከአባቆይታችን በወጣሁ ከአራት ዓመታት በኋላ ይሄ ሆነ። ሁሌ እሁድ እሁድ ከሰአት እንደማደርገው የሁለት አመት ተኩል ልጄን ማክዳን ይዤ ፣ ለእኔ እናትና አባቴ ፣ ለእሷ ደግሞ አያቷቿ ቤት ገባን።

ቆይታችን እንደ ሁሌ ነበር። አባዬ ማክዳን ጉልበቱ ላይ አሳፍሮ ይወዘውዛታል። ትስቃለች። እማዬ ለአምስት ሰው እንዲበቃ አድርጋ የሰራችውን ምግብ፣ ብቻዬን ጥርግ አድርጌ ስላልበላሁ ትነጫነጫለች።

እኔ ደግሞ አንዴ ቲቪ ላይ የምታወራውን ራኬብን፣ አንዴ ደግሞ በሣቅ የምትንፍቀፈቀውን ልጄን በስስት በፍቅር ዐያለሁ።

ዐስራ አንድ ሰአት ገደማ ሲሆን እንደተለመደው ቡና ቀራረበና ቤቱ መጫጫስ ጀመረ።

በእናቴ ''እንዲህ አድርጊ...እሱን...እጠቢ...ያኛውን አምጪ...ይሄንን ውሰጂ'' ታጅባ ቡናውን የምታፈላው ሰራተኛችን፣ ቴሌቪዢኑን እና ጀበናና ሲኒዎቿን አፈራርቃ እያየች በዝምታ ተቀምጣለች። ማክዳ እንቅልፍ ጥሏት የአባዬን ጋቢ ለብሳ ሶፋው ላይ ለጥ ብላለች።

እማዬና አባዬ የሳምንቱን ''አዳዲስ ወሬ'' በቡና እያወራሩዱ ያቀርቡልኝ ጀመር።

''ይሄ ሰፈር አሁንስ መላ ቅጡ ጠፋ፣ በቃ...! እንደሌላው ሰው ጨክነን ሸጠን መውጣት አለብን...'' አለ አባዬ። አባዬ በቀድሞው ሰላማዊ ሰፈራችን ''መበላሸት'' መማረሩ አዲስ አደለም። ይሄ ወሬ አግብቼ ከመውጣቴ በፊት በየቡናው የሚነሳና የሚጣል ነው። በመሰላቸት መታኘክ የማይፈልገውን ፈንዲሻዬን እንደማስቲካ አኝካለው
ቡናዬን ፉት እላለሁ።

''አሁንማ ለየለት እንጂ! ጭራሽ በራችን ላይ መቆም ጀመሩ እኮ!''

አለች እማዬ።

ይሄም የተለመደ ነገር ነው። የእማዬና የአባዬ ወሬ ልክ በካሴት ተቀርፆ ተደጋግሞ እንደሚሰማ ሁሉ ከጥቃት አረፍተ ነገሮች መቀዳደም ውጪ ሁሌም መገመት የሚችል ፤ ሁሌም አንድ ነው። በመታከት በወጉ ያልፈኩ ፈንዲሻዎችን ከሰሀኑ ላይ አፍሼ በጥርሴ ለመስበር እታገላለሁ። በመቀዝቀዝ ላይ ያለውን ቡናዬን ፉት እላለሁ።

''ሽጠን መሄድ አለብን ዝናሽ...በቀኝ ማሳጅ ቤት፣ በግራ መጠጥ ቤት ጎረቤት አድርገን እስከመቼ እንኖራለን....መሸጥ አለብን....!'' አባዬ ቀጠለ። ቀዝቃዛ ቡናዬን ጭልጥ አድርጌ ጨረስኩና ስኒውን ለልጅቱ ወሰድኩላት። ደንገጥ ብላ ብድግ አለችና ተቀበለችኝ፣

''ሦስተኛ ትተጫለሽ?'' አለችኝ።

''አይ... በቃኝ....'' አልኩና ቦታዬ ተመልሼ ተቀመጥኩ።

''እስቲ ሄለንዬ፣ ደህና ደላላ ፈልጌ...'' አለ አባዬ ቁጭ ከማለቴ።

''አይ አባ...'' አልኩና ዝም አለኩ።

''ምንድን ነዉ አይ አባ?'' ቆጣ ብሎ መለሰለኝ።

''የእናንተ ነገር እንሸጣለን ስትሉ ስንት ጊዚአችሁ ...እኔም....ዳግምም ስንት ደላላ አመጣንላችሉ....ዝም ብላችሁ ነው...'' አልኩኝ ሶፋዬ ላይ እየተመቻቸው።

''አይ....! አሁንስ በቅቶናል ሄለንዬ.. ትላንት የሆነውን ባየሽ ታምኚኝ ነበር!'' አለች እማዬ፣አለች እማዬ ስኒዋን ለልጅቷ እየመለሰች።

''ትላንት ደግሞ ምን ተፈጠረ?'' አልኩኝ ብዙ ሳልጓጓ።

ጡረተኞቹ እናትና አባቴ ትንሹን ትልቅ አድርገው የማየት አባዜ አለባቸው። ''መቼ እለት በራችን ላይ ትልቅ የመኪና አደጋ ተፈጥሮ ካሉ ፣ ሁለት ቪትዞች ተነካክተው ነበር ማለት ነው። ''አጎትሽ ነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ ላይ ነው '' ካሉ ሐኪም ቤት ውሎ ቤቱ ገብቷል ማለት ነው....

እማዬ ሰራተኛችንን አየት አደረገቻት። ሂጂ ማለቷ ነው። ሚስጥር ልናወራ ስለሆነ እቃሽን ሰብስበሽ ሂጂ ማለቷ ነው። ልጅቱ የሰው በማይመስል ፍጥነት እቃዎቿን በሙሉ ሰብስባ ወጣች።

አሁን ጓጓሁ።

''ምን ተፈጠረ ?'' አልኩ ደግሜ።

እማዬ የሚያጓጓ ወሬ ልትናገር ስትል እንደምትቀመጠው፤ ሰውነቷን ሁሉ ሶፏው ጫፍ ላይ ሰብስባ ተቀመጠችና ድምጿን ዝቅ አድርጋ፣ ማታ ማታ እዚህ ዋናው መግቢያችን.. አስፋልት ዳር የሚቆሙት ሴቶች የሉም?'' አለችኝ።

''እ...'' አልኩ ጉጉቴ እየናረ።

''ትላንት ማታ አምሽተን ስንመጣ ሺብሬን አያት!'' አባዬ ጭንቅላቱን ቀስ እያለ ግራና ቀኝ ወዘወዘ። ሲያዝን የሚያደርገው ነው።

''ሽብሬ...ሽብሬ የኛ?'' አልኩኝ ማመን እየተሳነኝ።

''እህስ!..ራሷ ናት። መኪናችንን ስታይ አወቀችን መሰለኝ ሸሽታ ብትሄድም በደንብ አይቻታለሁ!'' አለች እማዬ ከበፊቱ ጮክ ብላ። ''ከዚህ ከወጣች ወዲህ፣ ከእንግዲህ ሰው ቤት በቃኝ ብላ መሸታ ቤት እንደምትሰራ ሰምተን ነበር ግን እንዲህ ለይቶላታል ብዬ አላሰብኩም ነበር...አቤት አቤት!'' እማዬ ወደ ጣራ እያየች ተናገረች። ፈጣሪን ማየቷ ነው።

''ለነገሩ እንደዛ እንደልጃችን አድርገን ስናያት የሠራችንን ስራ ያየ ሰው መጨረሻዋ እንደዚህ ቢሆን አይደንቀውም...! ያሳዝናል ብቻ....''

አለ አባዬ።

ደነዘዝኩ።

ሺብሬ መጨረሻዋ እንዲህ ሆነ ? ስምንት አመት ወደ ኋላ ሄጄ የሆነውን ሁሉ አስታወስኩ።

ሞላሌ ከሚባል ሀገር መጥታ እኛ ቤት በሠራተኝነት ስትቀጠር ከዐስራ አምስት አመት አትበልጥም ነበር። እኔ ደግሞ ዐስራ ስምንት ሞልቶኝ ነበር። ፍልቅልቅ እና ደስተኛ፣ ገራገርና ታዛዥ ልጅ ነበረች።ከእኛ ቤት በፊት ሠራተኛ ሆና አታውቅም ሲሉ ትዝ ይለኛል። የተባለችውን ነገር በፍጥነትና በጥራት ትሠራ ስለነበር። እናቴ፣ ለእኔ በሚቀርብ መጠን ትወዳት ነበር ።

እኔ የተውኳቸው ልብስና ጫማዎች ይሰጧታል። ለዓመት በዓል ለእኔ አምስት ነገር ከተሰራ ለእሷ ደግሞ አንድ ነገር ይገዛላታል። የቤተሰብ ሽር ሽር ስንሄድ ሳይቀር ከእኔና ከወንድሜ ዳግም ጋር መኪና ውስጥ ቦታ ይኖራታል።

እንወዳት ነበር። እወዳት ነበር። ታናሼ ብትሆንም የምበላውን ሠርታ ስለምታቀርብልኝ፣ የምለብሰውን አጥባ ስለምትቶክስልኝ፤ የምተኛበትን አንጥፋ ስለምታሰናዳልኝ፣ የምወዳት እና የምትንከባከበኝ ታላቅ እህቴ ትመስለኝ ያህል እወዳት ነበር። ለዘላለም እኛ ቤት የምትኖር ይመስለን ነበር። እንደዚ ግን አልሆነም ለምን?

ሺብሬ እኛ ቤት በገባች በዓመት ከምናምኑ አባዬ ለእማዬ ለሃያኛ የጋብቻ በዓላቸው የገዛላት እና ድግሱ ላይ በመዐት ሰው ፊት የሰጣት የወርቅ ሀብል ጠፋ። በዚያ ግዜ ሦስት ሺህ አምስት መቶ ብር የፈጀ ሃብል ነበር።

እማዬ አቅሏን ሳተች። አበደች። አባዬ ብስጭቱ ከልክ አለፈ።

እኔ እና ዳግም ቃላችንን ሰጠን። በፊትም በጨዋነት ያሳደጓቸውና እስከዛሬ አንዲትም እቃ ንክች አድርገው የማያውቁት ጎረምሳ ልጆቻቸው በዚህ እንደማይጠረጠሩ የሚያውቁት እማዬና አባዬ ዐይናቸውን ማን ላይ ጣሉ? ያቺ መከረኛ ሽብሬ ላይ።

''ካንቺ ውጪ ማን ወሰደው ይባላል? እያዳፋሁ ፖሊስ ጣብያ ወስጄ ላስገርፍሽ ሃብሉን ውለጂ!'' ብለው አዋከቧት።

እንባዋ እስከዛሬ ትዝ ይለኛል።ከአንድ ሰው ዐይኖች በዚያ ፍጥነት ያ ሁሉ እንባ ሲወርድ፣ እስከዛሬ አላየሁም። ከማልቀስ ብዛት ዐይኖቿ ሽንቁር ያወጡ ይመስል ነበር።

በሀገሯ ታቦቶች ሁሉ ማለች፣ ተገዘተች። ግን ማንም አላመናትም። ክሯን ይዛ፣ ''ከዋሸሁ ሦስቱ ስላሴዎች እዚሁ ሦስት ቦታ ይቆራርጡኝ'' ብላ ማለች።ግን ማንም የሰማት አልነበረም። ከዚህ በኋላ የሆነው ሁሉ ባሰብኩት ቁጥር እንደ አዲስ ያመኛል። ከስምንት ዓመት በኋላም እንደ ትኩስ ቁስል ይመዘምዘኛል። እረፍት ይነሳኛል። እማዬና አባዬ እያካለቧት፣በእንግድነት የመጣው ዘመዳችን በእርግጫ እየመታት፣ ወንድሜ ዳግም ሌባ ብሎ እየጮኸባት፣ ፖሊስ ጣብያ ብለው ይዘዋት ሄዱ።

ቤቱ ውስጥ ብቻዬን ስሆን መኝታ ቤት ገባሁና አርቄ ፍራሼ ስር የደበኩትን የእማዬን የወርቅ ሀብል አውጥቼ ያዝኩትና ያለ ገደብ አነባሁ። አንድ ሺ ሰባት መቶ ብር
👍6
ልሸጠውና ከዝያ ግዜ ቦይፍሬዴ ቃልአብ ጋር፤ ''ልጫጫስበት'' የሰረኩትን የእማዬን የወርቅ ሃብል ይዤ ስቅስቅ ብዬ አለቀስኩ።

''ሽብሬ አይደለችም...እኔ ነኝ የሰረኩት'' ብዬ ለመናገር፣ ብዙ እድል ነበረኝ።

ዘመዳችን ስንት ግዜ ጎኖን በእርግጫ ሲያጎነው፣ ልነግራቸው እችል ነበር።

ዳግም ሌባ እያለ ሲያንባርቅባት፣ ልነግራቸው እችል ነበር።

ማተቧን ይዛ እያለቀሰች ስትገዘት፣ እማዬና አባዬ በመጠየፍ ሲመለከቷት፤ ''እሷ አይደለችም...እኔ ነኝ የሰረኩት'' ብዬ ልነግራቸው እችል ነበር። ግን አላደረኩትም።

...እና ዛሬ ሌባዋና ውሸታሟ ልጅ፤ የሞቀ ትዳር መስርቼ ስኖር፣ ያቺ ምስኪንና ሃቀኛ ልጅ ግን ሴት አዳሪ ሆና በልታ ለማደር መንገድ ላይ ወንድ ትጠብቃለች።😔

🔘አለቀ🔘

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
አትሮኖስ pinned «#አይ_ሽብሬ : : : አግብቼ ከእናት ከአባቆይታችን በወጣሁ ከአራት ዓመታት በኋላ ይሄ ሆነ። ሁሌ እሁድ እሁድ ከሰአት እንደማደርገው የሁለት አመት ተኩል ልጄን ማክዳን ይዤ ፣ ለእኔ እናትና አባቴ ፣ ለእሷ ደግሞ አያቷቿ ቤት ገባን። ቆይታችን እንደ ሁሌ ነበር። አባዬ ማክዳን ጉልበቱ ላይ አሳፍሮ ይወዘውዛታል። ትስቃለች። እማዬ ለአምስት ሰው እንዲበቃ አድርጋ የሰራችውን ምግብ፣ ብቻዬን ጥርግ አድርጌ…»
#ለእኔ_ያላት_እንጀራ
:
#በሕይወት_እምሻው
:
:
#ክፍል_አንድ
:
:
ሰው አይወጣልኝም።

በሠላሣ ሰባት አመቴ ህይወቴ ከጥቂት ሰዎች የተሰራ ነው።ሁለት በሠላሳዎቹ ዕድምዬ ያገኘኋቸው የልብ የማይባሉ ጓደኞች፣ እናቴ፣ አባቴ፣ አንድ ግማሽ እህት (አባቴ ከእናቴ በፊት የወለዳት) እና ጊዚያዊ ወንዶች።

እግዜር ከሰጠኝ ሰዎች ውጪ የእኔ ብዬ ያቆምኩትና የጸና የረጅም ጊዜ ግኑኝነት የለኝም። አብሬው አንድ በዐል ሁለት ጊዜ ያከበርኩት የወንድ ጓደኛ ኖሮኝ አያውቅም።

ሚስጥረኛ የለኝም።

የፍቅር ግኑኝነቶቼ አጭርና በጉድፍ የተሞሉ ናቸው። ይህ ሁሉ በልጅነቴ ያመንኩት ሰው ከድቶኝ፣ ወንድ አላምን ብዬ ምናምን አይደለም። እስከማምነው አብሮኝ የሚቆይ ወንድ አላገኘሁም እንተዋወቃለን። የተገግባባን እንመስላለን። ቡና፣ ማክያቶ እንባባላለነን። ክትፎ፣ በየአይነቱ እንገባበዛለን። ወይን፣ ቢራ አብረን እንጠጣለን። ቤርጎ ወይም ቤቱ ሄደን እንተኛለን። ከዚያ ሁሉ ነገር ይከስማል። ይጸድቃል የተባለው ይጠወልጋል። እንደ እሳት የተንቀለቀለው፣ በቀናት ወደ አመድነት ይለወጣል።

እንደሰው ባል የሚሆን ወንድ አግኝቼ መሰብሰብ፣ ልጅ ወልዶ መሳም ጠልቼ አይደለም። በጉልምስና እድሜዬ ፣ በሃያዎቹ መባቻ ላይ ሆና፣ ጊዜ ተርፏት እንደምትሽኮረመም እና ከአንዱ አንዱን የምታማርጥ ልጃገረድ፤ በየካፌው የማይረባ ማክያቶ የማንቃርረው ፣ በየቤርጎው ያልታጠበና ሌላ ሰው-ሌላ ሰው የሚሸት አንሶላ ላይ የምጋደመው፣ ሰው ፍለጋ ፤ ባል ባገኝ ብዬ ነው። ግን ሰው አልወጣልኝም።

ለዚህ ነው መስፍን የተለየብኝ።

መስፍኔ!

ቢሯችን ጨረታ ሊያስገባ መጥቶ ነው የተዋወቅነው። እንደታየሁ የወንድ ልብ ትርክክ የሚያደርግ ውበት፣ የሚያስደነብር ቁንጅና፣ እስቲ ስልክሽን አስብሎ የሚያስለምን ቁመና የለኝም። ግን መስፍን እንደሱ ሰራው።

ጨረታውን እንኳን ሳያስገባ ስምሽ ማነው ብሎ ጠየቀኝ።
''ማህደር....'' አልኩኝ። ትኩር ብለው የሚያዩኝን ዐይኖቹን ሽሽት፣ ጠረጴዛዬ ላይ ተመሳቅለው የተቀመጡትን ወረቀቶች እያየሁ። ከዛ ደግሞ ቀና ብዬ እያየሁት።

''ፐ....የሚያምር ስም ....l ማህ....ደር!'' አለ፣ አለ፣ ስሜን ሁለት ቦታ ከፍሎ። ስሜን እንዲህ ከወደደው፣ ስልክ ቁጥሬንማ በጣም ይወደዋል፣ ብዬ ለራሴ ቀልድ ነግሬ ራሴው ፈገግ ስል፣

''ምነው? ፊቴ ላይ የሚያስቅ ነገር አለ?'' አለኝ።

''አረ የለም.....''

''ወደሽኝ ነው?''

''ሆሆ....''

''ምነው የምወደድ አደለሁም?''

ሣቅኹ። የሚወደድ አይነት ነበር። ፍቅር ጀመርን።

ሁለት ወር በየቀኑ የሚባል መጠን እንገናኝ ነበር። ያልተገናኘንባቸውን ጥቂት ቀናትና ሰዓታት፣ በለሊት የስልክ ወሬዎች እንሞላቸው ነበር።

የምወደውን ስለሚወድ፣ የሚወደውን ስለምወድ፣ ሁሉ ነገር ቀላል ነበር።

ቲያትር ብንገባ ብዬ ያሰብኩ ቀን ቀድሞ፣''ዛሬ ትያትር እንይ'' ይለኛል።

የከቤ ኬክ ቤት ኬክ ውል ሲለኝ፣ ፊቴ ላይ የተፃፈ ይመስል፣ ''ዛሬ ኬክ አላመረሽም?'' እስቲ ከቤ ኬክ ወክ እናድርግ'' ይለኛል።

የሚወደድ አይነት ነበር። ትሁትና ደግ፣ ቁጥብና እርጋታ ያለው ሰው ነበር።

ብቻችንን ስንሆን ደግሞ ቁጥብነቱ ወደ ስግብግብነት ፣ እርጋታው ወደ የሚያስገርም ጥድፍያ...ደስ በሚል ሁኔታ ይለወጥ ነበር። በአደባባይ በትህትና እጆቼን ይዞ እንደማይጎዝ፣ ቤት ውስጥ ለፍቅር እያዘጋጀ ሲያቅፈኝ በመሀከላችን አየር እንኳን አያልፍም ነበር።

ከንፈሮቼን ተርቦ እህል እንዳገኘ ሰው ሲጎርሳቸው... እያንዳንዳቸው ዐሥር ጣት ያላቸው አምስት እጆች እንዳሉት ሀሉ፣ ልገምት በማልችለው ፍጥነት መላ ሰውነቴን አንድ በአንድ፣ ግን ደግሞ ባንድ ግዜ ሁሉም ቦታ ሲነካካኝ፣ ሲዳብሰኝ....ጀርባዬ ጋር ነው ስል ጭኖቼ ጋር፣ ጭኖቼ ጋር ስል ጡቶቼ ጋር .....ጡቶቼ ላይ ናቸው ስላቸው ጭኖቼ መሀል የሚገቡት እነዛ ጣቶቹ... እነዛ ለሦስት ሰው የሚበቁ ወፋፍራም ከንፈሮቹን አስተባብሮ ጆሮዬን እየሳመ ስሜን አጣፍጦ ሲያንሾካሹክ (ማ...ዲ...ዬ....ዬ) ፍቅር ሳንሰራ ጧ ብዬ የምፈነዳ ይመስለኝ ነበር።

ወ....ደ....ድ....ኩ.....ት።

እኔም በተራዬ ሰው ወጣልኝ። ስንቴ የተማለድኩት ፈጣሪዬ መስፍኔን ባል አድርጎ ሠርቶ ላከልኝ።

ግን ፈራሁ። ስለ መጋባት፣ ስለ ትዳር ወሬ ላወራው ፈራሁ። ግጣሜ መሆኑን ባውቅም፣ በሁለት ወር ውስጥ ብንጋባስ የሚል ሐሳብ ከአፌ አውጥቼ ማስደንበሩን ፈራሁ።

ግራ የሚያጋባ ሁኔታ ውስጥ ነበር ራሴን ያገኘሁት። ለጋብቻ የረፈደ እድሜዬን ሳስብ ስለ ጋብቻ አለማውራት አልችልም። ረፍዶብኛል። የሁለት ወር ግኑኝነታችንን ዕድሜ ሳስብ ግን ስለ ጋብቻ ማውራት አልችልም። መዋከብ ይሆናል። ብሽቅ ሁኔታ አይደለም?

ሁለቱን ጓደኞቼን አማከርኩ። ቤቲ በዘወትር ችኮላዋ፤

''ስንት አመቱ ነው?'' አለችኝ። ያልጠበቁት ጥያቄ ነበር።

''ስንት ዓመቱ ነው እሱ?'' ደገመችው።

''እ....እኔንጃ....''

''እንዴ! አታውቂም እንዴ ? ዕድሜውን ሳታውቂ ነው እስካሁን ላይ እታች የምትይው ?''

መስፍኔን ዕድሜውን በቀጥታ አልጠየኩትም። መጠየቅ ትልቅ ነገር ሆኖ ሳይሆን ያንን ጥያቄ የሚያስነሳ የወሬ ክር ስላልጀመርን ነው። አለ አይደል...ስለ ዶክተር አብይ ምናምን እያወራን ''ለመሆኑ አንተ እድሜክ ስንት ነው?'' አይባል ነገር ....

''አልጠየኩትም ግን መገመት እችላለሁ...'' አልኩ።

''እ....ስንት ነው?'' ቤቲ አሁንም በጥድፍያ ጠየቀችኝ።

''ኦኬ....ዩኒቨርስቲ ....ግራጅዌት ያረገው በ 92 ነው.....''

''በእኛ?''

''እንዴ ኦፍ ኮርስ በእኛ! ይሄን ያህል ሽማግሌ አረግሽው እንዴ!''

አልኩ እየሳኩ።

''የዛሬ ወንድ ምኑ ይታመናል! ለራሳቸው ሰርግ ሽማግሌ ሆነው መሄድ ሁሉ ጀምረዋል እኮ...'' ሁላችንም ሳቅን።

አፍታም ሳትቆይ ቤቲ ስልኳን ከቦርሳዋ በፍጥነት አወጣች መስፍኔ በሌለበት እድሜው ሊሰላለት ነው። ጎንበስ ብላ ጠቅ ጠቅ አድርጋ ቀና ብላ ዐየችኝና፣

''የአዲስ አበባ ልጅ ነው?'' አለችኝ። ግር ብሎኝ...

''እሱ ደግሞ እድሜው ውስጥ ምናገባው?'' አልኳት።

''እንዴ.... የገጠር ልጅ ከሆነ ትምህርት ቶሎ ስለማይጀምር፣ አንድ አምስት ልጨምርበት ነዋ!'' ብላ ስትስቅ ፣ እስካሁን ዝም ብላ የነበረችው ሄዋንም አጀበቻት።

''ወይ ጉድ...ያንቺ ጉድ ብዙ ነው....የአራት ኪሎ ልጅ ነው....''

አልኩ።

''ፈይን እንግዲህ ሁለት ሺ አስራ አንድ ገባን አይደል...በሃያ ሁለት ዓመቱ ጨረሰ ብንል እንኳን፤ አርባ አንድ ወይ አርባ ሁለቱን ጠጥቷል ማለት ነው!'' አለችና፣ ትልቅ ሚስጢር ቆፍሮ እንዳገኘ ሰው ኮራ ብላ ሦስት ጊዜ አጨበጨበች።

ከግምቴ ብዙም የራቀ ስላልነበር አልተገረምኩም

''እሺ...እድሜው ይሁንና ምንድን ነው የምትመክሩኝ?'' አልኩ ቤቲንም ሄዋንንም እያየሁ። ሄዋን ንግግሯን ለመጀመር አፏን ስትከፍት ቤቲ ቀደመቻትና፤

''እኔ ጠይቂውና ያበጠው ይፈንዳ ነው የምለው...እሱም ትልቅ ሰው ነው ደግሞ...ከማይሆን ሰው ጋር ጊዜሽን ዌስት የምታደርጊበት ዕድሜ ላይ አይደለሽም....በዛ ላይ አሪፍ ነው ምናምን ብለሻል...እና.... ጠይቂው ባይ ነኝ።'' አለችኝ ምክሯ አልገረመኝም። የቤቲ የኑሮ ዘይቤ ችኮላና ያበጠው ይፈንዳ ነው። ፍጥነት ነው። ዛሬን መኖር ነው።

ሄዋንን አየኋት።

💫ይቀጥላል💫

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍71🥰1
አትሮኖስ pinned «#ለእኔ_ያላት_እንጀራ : #በሕይወት_እምሻው : : #ክፍል_አንድ : : ሰው አይወጣልኝም። በሠላሣ ሰባት አመቴ ህይወቴ ከጥቂት ሰዎች የተሰራ ነው።ሁለት በሠላሳዎቹ ዕድምዬ ያገኘኋቸው የልብ የማይባሉ ጓደኞች፣ እናቴ፣ አባቴ፣ አንድ ግማሽ እህት (አባቴ ከእናቴ በፊት የወለዳት) እና ጊዚያዊ ወንዶች። እግዜር ከሰጠኝ ሰዎች ውጪ የእኔ ብዬ ያቆምኩትና የጸና የረጅም ጊዜ ግኑኝነት የለኝም። አብሬው አንድ በዐል…»