...ትንሽ ቦት...
በዚህ አመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ትንሽ በታ መጠለያ
ትንሽ ቦታ መሰደጃ
ምናለበት፣
ለምን አልባት ብንተውለት
ፍፁም መሆን ስለማንችል
ትንሽ ባዶ እንዋዋል፣በልባችን ደግ በኩል
በአንጎላችን መላወሻ
ትንሽ ቦታ እንተውለት
"ምን አልባት" የምንልበት
ልክ እንደ አምና ለዚህ አመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ብንታሰር ይቅር ማያ
ይቅር ብንል መታሰሪያ
ትንሽ እንተው ባዶ ቦታ
ጥግ ድረስ ባለን ስፍራ ጥግ ድረስ የለም ፋታ
በልባችን ደግ በኩል እንፈልግ ባዶ ቦታ
የጳጉሜ አይነት ትንሽ ቦታ
ለዘመን መለወጫ።
በነብይ መኮነን
በዚህ አመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ትንሽ በታ መጠለያ
ትንሽ ቦታ መሰደጃ
ምናለበት፣
ለምን አልባት ብንተውለት
ፍፁም መሆን ስለማንችል
ትንሽ ባዶ እንዋዋል፣በልባችን ደግ በኩል
በአንጎላችን መላወሻ
ትንሽ ቦታ እንተውለት
"ምን አልባት" የምንልበት
ልክ እንደ አምና ለዚህ አመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ብንታሰር ይቅር ማያ
ይቅር ብንል መታሰሪያ
ትንሽ እንተው ባዶ ቦታ
ጥግ ድረስ ባለን ስፍራ ጥግ ድረስ የለም ፋታ
በልባችን ደግ በኩል እንፈልግ ባዶ ቦታ
የጳጉሜ አይነት ትንሽ ቦታ
ለዘመን መለወጫ።
በነብይ መኮነን
👍1
የባከነ ሌሊት!!!!
ወይ ሮንድ አላደርኩ
ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ
ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ
ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ
የባለጌ ወንበር :ኮርቻ አልተሳፈርሁ
ወይ ሰአታት ቁሜ
ቤተክስያን ስሜ
ሰይጣን አላሳፈርሁ::
ሌቦች ደብድበውት
አንዱን ምስኪን ላሥር
ባምቢስ ድልድዩ ሥር
ቆስሎ የወደቀ
ገላው በላዩ ላይ :እንደጨርቅ ያለቀ
ፊቱ ተሸፍኖ : በደምና አቧራ
"በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ
ምስኪን አባወራ
ብብት ሥር ገብቼ
አፋፍሼ አንስቼ
ተሸክሜ አድኜ
ስፈልግ አምቡላንስ :ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ
ወይ ምግባር አልሠራሁ
ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ : ወይ ፅድቅ አላፈራሁ::
አንድ በትረ-ሙሴ
ሁለት ስስ አሎሎ
ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ
ሲባክን ዝምብሎ
" እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ"
የምትል መለሎ
ልቤን ሳትሰውረው
አልጋየን ሳትሰብረው::
ወግ ቢጤ ሞንጭሬ: ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ
" እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ::
አንዲት ሴት- አዳሪ :ቺቺንያ ምንገድ ላይ
እድሉዋ ሰባራ :ሰውነቱዋ አማላይ
ካፍያውና እንባዋ : ተጋግዞ ሚያረጥባት
ደምበኛ ስትጠበቅ :ደመኛ ጥሎባት
አምስት ደፋሪዎች : ከበው ሲያዋክቧት
ሲገፉ ሲስቧት
" እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን
እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን
ልመናዋ ስቦኝ
እንዳበጀ በለው : በደሏ አንገብግቦኝ
ከሁዋላ ደርሼ
ነበልባል ለብሼ: ነበልባል ጎርሼ
እንደብሩስሊ: እንዳየሩ ጋኔን
እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ
ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን
በማረግ ቃኝቼ
ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ
ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ
ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ::
ድል ሳላስመዘግብ
ውጥረት ሳለረግብ
ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ
ያለምንም ጣጣ : ያለምንም ፀጋ
አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ::
በውቀቱ ስዩም
ወይ ሮንድ አላደርኩ
ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ
ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ
ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ
የባለጌ ወንበር :ኮርቻ አልተሳፈርሁ
ወይ ሰአታት ቁሜ
ቤተክስያን ስሜ
ሰይጣን አላሳፈርሁ::
ሌቦች ደብድበውት
አንዱን ምስኪን ላሥር
ባምቢስ ድልድዩ ሥር
ቆስሎ የወደቀ
ገላው በላዩ ላይ :እንደጨርቅ ያለቀ
ፊቱ ተሸፍኖ : በደምና አቧራ
"በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ
ምስኪን አባወራ
ብብት ሥር ገብቼ
አፋፍሼ አንስቼ
ተሸክሜ አድኜ
ስፈልግ አምቡላንስ :ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ
ወይ ምግባር አልሠራሁ
ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ : ወይ ፅድቅ አላፈራሁ::
አንድ በትረ-ሙሴ
ሁለት ስስ አሎሎ
ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ
ሲባክን ዝምብሎ
" እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ"
የምትል መለሎ
ልቤን ሳትሰውረው
አልጋየን ሳትሰብረው::
ወግ ቢጤ ሞንጭሬ: ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ
" እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ::
አንዲት ሴት- አዳሪ :ቺቺንያ ምንገድ ላይ
እድሉዋ ሰባራ :ሰውነቱዋ አማላይ
ካፍያውና እንባዋ : ተጋግዞ ሚያረጥባት
ደምበኛ ስትጠበቅ :ደመኛ ጥሎባት
አምስት ደፋሪዎች : ከበው ሲያዋክቧት
ሲገፉ ሲስቧት
" እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን
እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን
ልመናዋ ስቦኝ
እንዳበጀ በለው : በደሏ አንገብግቦኝ
ከሁዋላ ደርሼ
ነበልባል ለብሼ: ነበልባል ጎርሼ
እንደብሩስሊ: እንዳየሩ ጋኔን
እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ
ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን
በማረግ ቃኝቼ
ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ
ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ
ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ::
ድል ሳላስመዘግብ
ውጥረት ሳለረግብ
ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ
ያለምንም ጣጣ : ያለምንም ፀጋ
አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ::
በውቀቱ ስዩም
👍1👏1
#አንቺ #ሰትስሚኝ😘
የምትዞርው አለም ባንዴ ትቆማለች
እሩቁዋ ጨርቃ ያኔ ትቀርባለች
ምድርም የዛኔ በእኛ ትደምቃለች ........................ ታሸበርቃለች
ልጆችዋ ነን እና እኛን ትድራለች አንቺ ሰትስሚኝ!!!!! ከተራራ እንደ መውደቅ ሰልጣን እንደ መልቀቅ ተሰቅሎ እንደ መታነቅ ሱሪ እንደ መውለቅ
ነብሴ ትጨነቃለች ልቤ ትመታለች አንቺን አንቺን ፍቅርን ትፈራለች አንቺ ሰትስሚኝ!!!!! ሞቶ እንደ መነሳት የወደቀ እንደ ማንሳት በጥይት እንደ መሳት ችግር እንደ መርሳት
ህይወቴ ታድሳ ብሩህ ትሆናለች
ጎዶሎዋ አለም ያኔ ትሞላለች አንቺ ሰትስሚኝ!!!!
ወፎች ያዜማሉ ኮዋክብት ይርግፍሉ
አማልክት ይወርዳሉ አራዊት ይታደማሉ
መንግሰታት መግደል ያቆማሉ ................ታክሲዋች ይጭናሉ ...............አዋቂዋች ይታዘላሉ
.................ነጋዴዋች ያተርፋሉ አንቺ ሰትስሚኝ!!!! ጽልመት ይባርራል ሰልጣንም ያርጃል
ህፃን ልጅም ያድጋል ግጥምም ያልቃል
የምትዞርው አለም ባንዴ ትቆማለች
እሩቁዋ ጨርቃ ያኔ ትቀርባለች
ምድርም የዛኔ በእኛ ትደምቃለች ........................ ታሸበርቃለች
ልጆችዋ ነን እና እኛን ትድራለች አንቺ ሰትስሚኝ!!!!! ከተራራ እንደ መውደቅ ሰልጣን እንደ መልቀቅ ተሰቅሎ እንደ መታነቅ ሱሪ እንደ መውለቅ
ነብሴ ትጨነቃለች ልቤ ትመታለች አንቺን አንቺን ፍቅርን ትፈራለች አንቺ ሰትስሚኝ!!!!! ሞቶ እንደ መነሳት የወደቀ እንደ ማንሳት በጥይት እንደ መሳት ችግር እንደ መርሳት
ህይወቴ ታድሳ ብሩህ ትሆናለች
ጎዶሎዋ አለም ያኔ ትሞላለች አንቺ ሰትስሚኝ!!!!
ወፎች ያዜማሉ ኮዋክብት ይርግፍሉ
አማልክት ይወርዳሉ አራዊት ይታደማሉ
መንግሰታት መግደል ያቆማሉ ................ታክሲዋች ይጭናሉ ...............አዋቂዋች ይታዘላሉ
.................ነጋዴዋች ያተርፋሉ አንቺ ሰትስሚኝ!!!! ጽልመት ይባርራል ሰልጣንም ያርጃል
ህፃን ልጅም ያድጋል ግጥምም ያልቃል
ውድ የቻናላችን ተከታዮች በዳንኤል ሰቲል ተፅፎ በአብይ ደምሴ የተተረጎመውን ብርቅርቅታ የተሰኘውን ቆየት ያለ መፅሐፍ ያላነበበው ካለ ሙሉውን በPdf ቀርቦላችኋል መልካም ንባብ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
አዝዤ ልጎርሰው፥
ያጠቀስኩት ሽሮ፥ አፌን ገፍቶ ይርቃል
ማባያ የሰነግኩት፥
አረንጓዴ ቃርያ፥ በቅፅበት ይደርቃል
እንደ በረኅ ምድር፥
እንጀራዬ ከስሎ፥ ይሰነጣጠቃል።
ጆሮዬ ከፒያሳ፥
ቦሌ እሚንቆረቆር፥ ይሰማዋል ድራፍት
አይኔ ካራት ኪሎ፥
ቄራ የሚፈረሽ፥ ይታየዋል ፍትፍት።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
ያበዳሪን ሰፈር፥
በጀግና አረማመድ፥ ሄዳለሁ ሰንጥቄ
የቡቲኩን ጌታ፥
የጃኬቱን ዋጋ፥ አልፋለሁ ጠይቄ
ስቸስት የከዳኝ፥
ወዳጄን ፈልጌ፥ አልሳለሁ ጥፊ
እንዳያዩኝ ብዬ፥
ከተደበቅኋቸው፥
ካ'ከራዬ ጋራ፥ እነሳለሁ ሰልፊ።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
ኤድናሞል ደጃፍ፥ ላይ እንጎራደዳለሁ...
ቮድካ እንኳ ባይገኝ፥
የሜንት ያ'ፕሬቲቭ፥ ቦትል አወርዳለሁ
ባለረዥም ፀጉር፥
ባለ ለስላሳ ድምፅ፥ ባለ አይን ባለ አንገት
እያልኩ የተውኳቸው፥
የቸከሶቼ ስልክ፥ ትዝ ይለኛል ድንገት።
ፀሃይ ሲያዘቀዝቅ፥
እያንገሸገሸኝ፥
እያንቀጠቀጠኝ፥ ፀጥ ያለው ሰፈሬ
ወደ ሃያሁለት፥
ቦሌ መድሃኒያለም፥
ወደ አትላስ ጀርባ፥ይመራኛል እግሬ።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
አዝዤ ልጎርሰው፥
ያጠቀስኩት ሽሮ፥ አፌን ገፍቶ ይርቃል
ማባያ የሰነግኩት፥
አረንጓዴ ቃርያ፥ በቅፅበት ይደርቃል
እንደ በረኅ ምድር፥
እንጀራዬ ከስሎ፥ ይሰነጣጠቃል።
ጆሮዬ ከፒያሳ፥
ቦሌ እሚንቆረቆር፥ ይሰማዋል ድራፍት
አይኔ ካራት ኪሎ፥
ቄራ የሚፈረሽ፥ ይታየዋል ፍትፍት።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
ያበዳሪን ሰፈር፥
በጀግና አረማመድ፥ ሄዳለሁ ሰንጥቄ
የቡቲኩን ጌታ፥
የጃኬቱን ዋጋ፥ አልፋለሁ ጠይቄ
ስቸስት የከዳኝ፥
ወዳጄን ፈልጌ፥ አልሳለሁ ጥፊ
እንዳያዩኝ ብዬ፥
ከተደበቅኋቸው፥
ካ'ከራዬ ጋራ፥ እነሳለሁ ሰልፊ።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
ኤድናሞል ደጃፍ፥ ላይ እንጎራደዳለሁ...
ቮድካ እንኳ ባይገኝ፥
የሜንት ያ'ፕሬቲቭ፥ ቦትል አወርዳለሁ
ባለረዥም ፀጉር፥
ባለ ለስላሳ ድምፅ፥ ባለ አይን ባለ አንገት
እያልኩ የተውኳቸው፥
የቸከሶቼ ስልክ፥ ትዝ ይለኛል ድንገት።
ፀሃይ ሲያዘቀዝቅ፥
እያንገሸገሸኝ፥
እያንቀጠቀጠኝ፥ ፀጥ ያለው ሰፈሬ
ወደ ሃያሁለት፥
ቦሌ መድሃኒያለም፥
ወደ አትላስ ጀርባ፥ይመራኛል እግሬ።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
👍4
፨ዘመም ይላል እንጂ፨
እንደ ጊዜው መክፋት
እንደ ግፉ መስፋት
እንዳገሩ ክስመት
እንዳገሬው ጥመት
እንደሰው ጭካኔ፤ እንደ ልቡ ፍሬ
ታምር ነው መትረፍሽ ፤ ታምር ነው መኖሬ::
የበጎ ሰው ሀሳብ ፤ ሲካድ እለት በለት
ጉድጏድ ተምሶለት
ሰብእና ሲቀበር፤
በዚህ ምድር መኖር ፤ አያስመኝም ነበር::
ምድሩ ሳር ቅጠሉ፤ በስጋት ተሞልቶ
የማለዳው ሰማይ፤ እንዳንቀልባ ቀልቶ
ታረደ
ነደደ
ከዘብጥያ ወጥቶ
ዘብጥያ ወረደ
የሚል ዜና ብቻ አየሩን ሲሞላው
ሰው በገዛ ጥላው
በርግጎ ሲሸበር
በዚህ ምድር መኖር ፤አያስመኝም ነበር::
አዎ
ለጊዜውም ቢሆን፤ ግፍ ያደነዝዛል
በደል ያስተክዛል
ጊዜም ጠብን ሽሮ፤ ወደ ፊት ይጏዛል
በልብ ሰሌዳ ላይ ፤ቂም ይደበዝዛል
በነገ ያመነ
ልጁን ቀብሮ መጥቶ፤ ሚስቱን ያስረግዛል::
ይቅርታና ምህረት
ፍቅርና ህብረት
ከግፍ ጋር ፍልሚያቸው ፤ ቢሆን የሞት ሽረት
ዳገት ይወጣሉ ፤ በንጥፍጣፊ አቅም
የመኖር ፍላጎት
ዘመም ይላል እንጂ ፤ ተገርስሶ አይወድቅም::
((በውቀቱ ስዩም))
እንደ ጊዜው መክፋት
እንደ ግፉ መስፋት
እንዳገሩ ክስመት
እንዳገሬው ጥመት
እንደሰው ጭካኔ፤ እንደ ልቡ ፍሬ
ታምር ነው መትረፍሽ ፤ ታምር ነው መኖሬ::
የበጎ ሰው ሀሳብ ፤ ሲካድ እለት በለት
ጉድጏድ ተምሶለት
ሰብእና ሲቀበር፤
በዚህ ምድር መኖር ፤ አያስመኝም ነበር::
ምድሩ ሳር ቅጠሉ፤ በስጋት ተሞልቶ
የማለዳው ሰማይ፤ እንዳንቀልባ ቀልቶ
ታረደ
ነደደ
ከዘብጥያ ወጥቶ
ዘብጥያ ወረደ
የሚል ዜና ብቻ አየሩን ሲሞላው
ሰው በገዛ ጥላው
በርግጎ ሲሸበር
በዚህ ምድር መኖር ፤አያስመኝም ነበር::
አዎ
ለጊዜውም ቢሆን፤ ግፍ ያደነዝዛል
በደል ያስተክዛል
ጊዜም ጠብን ሽሮ፤ ወደ ፊት ይጏዛል
በልብ ሰሌዳ ላይ ፤ቂም ይደበዝዛል
በነገ ያመነ
ልጁን ቀብሮ መጥቶ፤ ሚስቱን ያስረግዛል::
ይቅርታና ምህረት
ፍቅርና ህብረት
ከግፍ ጋር ፍልሚያቸው ፤ ቢሆን የሞት ሽረት
ዳገት ይወጣሉ ፤ በንጥፍጣፊ አቅም
የመኖር ፍላጎት
ዘመም ይላል እንጂ ፤ ተገርስሶ አይወድቅም::
((በውቀቱ ስዩም))
#የማሪያም #ንግስ #ዕለት
.
.
.
የማርያም ንግስለት
አዳፋ ነጠላ
በቀጠነ ገላ ÷ነፋስ የሚጥለው
የነተበ ጫማ
ጥቁር ያዘን ቀሚስ ÷ኑሮ ያጨቀየው
ለብሳ የተገኘች ,,,,,,
ከቤተስኪያን አጸድ —ቆማ ከዋርካውስር
አንዲት ምስኪን ባልቴት —,,,,,ትለማመንነበር
አደራሽ ን ማርያም
አደራሽን ማርያም
እበላው የለኝ መሶ ቤ ተራቁቷል
እለብሰው የለኝም ጀረረባዬ በርዶታል ።
ወድቃ የተነሳች
እንባ ያፈሰሰች
ተስፋዋ ማርያምን ትለምናት ነበር
ከቤተስኪያን ጓሮ ቆማ ከዋርካው ስር ።
*
የደብሩ አለቃ
ካ ባ ላንቃ ለብሶ ሞጣህቱን ደርቦ
ልክ የሌለው ቦርጬ ወደፊት ተስቦ
ጮክ ብሎ ያወራል
ጮክብሎ ያስተምራል ።
1
የመቅደሱ ቀለም ሊታደስ ይገባል
2
የካህናት ደሞዝ ሊጨመር ይገባል
3
ደጀ ሰላም ወንበር እጅጉን ያንሰናል ,,,,
እናም ,,,
በዚህ ታላቅ ደብር ይህ ችግር ስላለ
ለማርያም የሚሆን እ ጃችሁ የታለ ?
እያለ ።,,,,
ህዝቡን ያስተምራል
ህዝቡን ይደልላል ።
ለንግሱ የመጡ
ባለ ብዙ ብሮች
ብዙ ባለጠጎች
ጥለት የለበሱ በሽቶ የራሱ
ቆመው የነበሩ እፊት ተመቅደሱ
ቀለም እንዲቀባ እንዲታደስ ደብሩ
ለደጀ ሰላሙ ደግሞም ለወንበሩ
በ ሺ ሚቆጠሩ
ብሮች ወረወሩ
የደብሩ አለቃ ግንባር በጣም ወዛ
የሚወረው ብሩም በጣም በዛ
*
የዛች የየምስኪን ነብስ
ያቺ ታላቅ መቅደስ
ቆማ ከዋርካስር
ተስፋዋ ማርያምን ትለማመን ነበር
አደራሽን ማርያም
አደራሽን ማርያም
እበላው የለኝም መሶቤ ተራቁቷል
እጠጣው የለኘኝም ማድጋዬ ጓድሏል
እለብሰው የለኝም ጀርባዬን በርዶታል
አንቺው ነሽ ተስፋዬ የኔ ተስፋ ሞቷል
ወድቃ የተነሳች
እንባ ያፈሰሰች ።
ግና —ግን ለዛሬ —ለክብርሽ እንዲሆን
ተቀበይ ስጦታ ውሰጅ አማሀዬን
የሟች ባሌን ማስታወሻ የአንገት ሃብሌን፡፡
በኤፍሬም ስዩም
.
.
.
የማርያም ንግስለት
አዳፋ ነጠላ
በቀጠነ ገላ ÷ነፋስ የሚጥለው
የነተበ ጫማ
ጥቁር ያዘን ቀሚስ ÷ኑሮ ያጨቀየው
ለብሳ የተገኘች ,,,,,,
ከቤተስኪያን አጸድ —ቆማ ከዋርካውስር
አንዲት ምስኪን ባልቴት —,,,,,ትለማመንነበር
አደራሽ ን ማርያም
አደራሽን ማርያም
እበላው የለኝ መሶ ቤ ተራቁቷል
እለብሰው የለኝም ጀረረባዬ በርዶታል ።
ወድቃ የተነሳች
እንባ ያፈሰሰች
ተስፋዋ ማርያምን ትለምናት ነበር
ከቤተስኪያን ጓሮ ቆማ ከዋርካው ስር ።
*
የደብሩ አለቃ
ካ ባ ላንቃ ለብሶ ሞጣህቱን ደርቦ
ልክ የሌለው ቦርጬ ወደፊት ተስቦ
ጮክ ብሎ ያወራል
ጮክብሎ ያስተምራል ።
1
የመቅደሱ ቀለም ሊታደስ ይገባል
2
የካህናት ደሞዝ ሊጨመር ይገባል
3
ደጀ ሰላም ወንበር እጅጉን ያንሰናል ,,,,
እናም ,,,
በዚህ ታላቅ ደብር ይህ ችግር ስላለ
ለማርያም የሚሆን እ ጃችሁ የታለ ?
እያለ ።,,,,
ህዝቡን ያስተምራል
ህዝቡን ይደልላል ።
ለንግሱ የመጡ
ባለ ብዙ ብሮች
ብዙ ባለጠጎች
ጥለት የለበሱ በሽቶ የራሱ
ቆመው የነበሩ እፊት ተመቅደሱ
ቀለም እንዲቀባ እንዲታደስ ደብሩ
ለደጀ ሰላሙ ደግሞም ለወንበሩ
በ ሺ ሚቆጠሩ
ብሮች ወረወሩ
የደብሩ አለቃ ግንባር በጣም ወዛ
የሚወረው ብሩም በጣም በዛ
*
የዛች የየምስኪን ነብስ
ያቺ ታላቅ መቅደስ
ቆማ ከዋርካስር
ተስፋዋ ማርያምን ትለማመን ነበር
አደራሽን ማርያም
አደራሽን ማርያም
እበላው የለኝም መሶቤ ተራቁቷል
እጠጣው የለኘኝም ማድጋዬ ጓድሏል
እለብሰው የለኝም ጀርባዬን በርዶታል
አንቺው ነሽ ተስፋዬ የኔ ተስፋ ሞቷል
ወድቃ የተነሳች
እንባ ያፈሰሰች ።
ግና —ግን ለዛሬ —ለክብርሽ እንዲሆን
ተቀበይ ስጦታ ውሰጅ አማሀዬን
የሟች ባሌን ማስታወሻ የአንገት ሃብሌን፡፡
በኤፍሬም ስዩም
👍3
😁ደስታን ፍለጋ😁
በግምት ወደ 50 ሰው የሚይዝ ህብረት በአንድ አዳራሽ ለጥብቅ ጉዳይ ይሰባሰባሉ::ፕሮግራሙ ከመጀመሩ በፊት መድረክ መሪው ታዳሚዎችን አንድ ጫወታ ሊያጫውት ይወስናል::በአዳራሹ ለተሰበሰቡ ሰዎች አንዳንድ ፊኛ ሰጥቷቸው ስማቸውን በእስክሪብቶ ፊኛው ላይ እንዲፅፉበት ያዛቸዋል::
ሁሉም ፅፈው ከጨረሱ በሁዋላ ፊኛው ተሰብስቦ በአንድ ጠባብ ክፍል ውስጥ ተበታትኖ እንዲቀመጥ ያደርጋል::በመቀጠል ጫወታው በ5 ደቂቃ ጠባቧ ክፍል ውስጥ ተበታትኖ ከተቀመጠው ፊኛ እያንዳንዳቸው ስማቸው የተፃፈበትን ፊኛ አግኝቶ መመለስ ነው ተባለ::በቅፅበት ያቺ ክፍል ስማቸውን በሚፈልጉ ታዳሚዎች ትርምስምስዋ ወጣ::ነገር ግን በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ትዕዛዙን ተግብሮ ስሙን ያገኘ አንድ እንኳን አልነበረም::የጫወታው አስተባባሪም ከመድረክ ወጥቶ 1 ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ለሀምሳዎቹም ፊኛቸው ስማቸውን እየጠራ መለሰ:: ደስታም እንዲህ ናት::በዚህች ጠባብ እና በማይሞላላት አለም ትውልድ ከሌላው ይልቅ የራሱን ደስታ ፍለጋ ይተራመሳል!!
ነገር የደስታን መገኛ በቅጡ አላወቀም::
አትጠራጠሩ በክፍሉ ውስጥ መጀመርያ ያገኙትን ፊኛ ለስሙ ባለቤት እየጠሩ ቢሰጣጡ ልክ እንደመድረኩ 1 ደቂቃ አይፈጅባቸውም ነበር::
ስለዚህ የእርሶን ደስታ ማግኘት ይሻሉ ??
የሌላ ሰው ደስታ በእጅዎ ነውና ይመልሱ ያን ጊዜ የእርሶ የሆነ ነገር ወደ እጅዎ ለመግባ ጊዜ አይፈጅም!!! ደስተኛ ቀን ተመኘሁ
በግምት ወደ 50 ሰው የሚይዝ ህብረት በአንድ አዳራሽ ለጥብቅ ጉዳይ ይሰባሰባሉ::ፕሮግራሙ ከመጀመሩ በፊት መድረክ መሪው ታዳሚዎችን አንድ ጫወታ ሊያጫውት ይወስናል::በአዳራሹ ለተሰበሰቡ ሰዎች አንዳንድ ፊኛ ሰጥቷቸው ስማቸውን በእስክሪብቶ ፊኛው ላይ እንዲፅፉበት ያዛቸዋል::
ሁሉም ፅፈው ከጨረሱ በሁዋላ ፊኛው ተሰብስቦ በአንድ ጠባብ ክፍል ውስጥ ተበታትኖ እንዲቀመጥ ያደርጋል::በመቀጠል ጫወታው በ5 ደቂቃ ጠባቧ ክፍል ውስጥ ተበታትኖ ከተቀመጠው ፊኛ እያንዳንዳቸው ስማቸው የተፃፈበትን ፊኛ አግኝቶ መመለስ ነው ተባለ::በቅፅበት ያቺ ክፍል ስማቸውን በሚፈልጉ ታዳሚዎች ትርምስምስዋ ወጣ::ነገር ግን በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ትዕዛዙን ተግብሮ ስሙን ያገኘ አንድ እንኳን አልነበረም::የጫወታው አስተባባሪም ከመድረክ ወጥቶ 1 ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ለሀምሳዎቹም ፊኛቸው ስማቸውን እየጠራ መለሰ:: ደስታም እንዲህ ናት::በዚህች ጠባብ እና በማይሞላላት አለም ትውልድ ከሌላው ይልቅ የራሱን ደስታ ፍለጋ ይተራመሳል!!
ነገር የደስታን መገኛ በቅጡ አላወቀም::
አትጠራጠሩ በክፍሉ ውስጥ መጀመርያ ያገኙትን ፊኛ ለስሙ ባለቤት እየጠሩ ቢሰጣጡ ልክ እንደመድረኩ 1 ደቂቃ አይፈጅባቸውም ነበር::
ስለዚህ የእርሶን ደስታ ማግኘት ይሻሉ ??
የሌላ ሰው ደስታ በእጅዎ ነውና ይመልሱ ያን ጊዜ የእርሶ የሆነ ነገር ወደ እጅዎ ለመግባ ጊዜ አይፈጅም!!! ደስተኛ ቀን ተመኘሁ
👍2
#እንደምነሽ #ሸገር
በውቀቱ ስዩም ከአሜሩካ
እንደምነሽ ሸገር የቤት አከራዬ የጋሽ ጣሰው አገር የምትተከዪ የምትነቀዬ የዘመቻ ድንኳን
ብጉርና ችግር ከአባቴ ወርሼ ብኖርብሽ እንኳን
የማልቀያምሽ ሁሌ የማልምሽ
ኦ ማይ ጎድ ይመስገን እኔ እንዳለሁ አለው
ግማሽ እሩዝና ግማሽ ጤፍ በልቼ
አዋጅ እና ዜና ከአደባባይ ሳይሆን ከአይፎኔ ሰምቼ
ሀሜት ሲናፍቀኝ በስካይፒ አምቼ
ጥቃት ሲሰማኝ ፊስቡክ ላይ ሸፍቼ
በኮመንት እሩምታ ጠላቴን ደፍቼ
እኔ እንዳለው አለው
እንደምነሽ ሸገር እንደምነሽ ሸገር
የማይበገረው ወር እየጠበቀ የሚያገራግረው
የቤት አከራዬ የጋሽ ጣሰው አገር
የከሰመው ወንዝሽ የሚታየው ነጥፎ
እንደምነው ጣፎ እንዴት ነው ቀበና
እስቲ ድንጋይ ላጥምድ መረብ ልጣልና
ልክ እንደነ ፓሪስ እንደለንደን ሁላ
ፋፋቴም ባይኖርሽ ሽቅብ የሚፈላ
ምንጭሽ ከማን ያንሳል
ከፈነዳ ትቦ የወጣ ሰገራ ሰንጥቆሽ ይፈሳል
እንደምነሽ ሸገር የቅጠላቅጠል የፍራፍሬ አገር
አንድ ዘለላ ሙዝ ልጠሽ ባታበይኝ
በሙዝ ልጣች ጠልፈሽ የምታከባልይኝ
አሳድገሽኛል አሳድገሽኛል በማርና ወተት
የተሞላ ተረት እየተረክሽልኝ
ጥማቴን በጥማት እያረካሽልኝ
እንደምነሽ ሸገር ኦ ማይ ጎድ ይመስገን
እኔ እንዳለው አለው ሰርቼ ቀፍዬ
ሲነጋ ቀፍዬ ሲመሽም ከፍዬ
ስጋ ምታወፍር ነብስ የምታሳሳ
ዘናጭ አልጋ ሰታ እንቅልፍ የምትነሳ
አገር ላይ ተጥዬ
በውቀቱ ስዩም ከአሜሩካ
እንደምነሽ ሸገር የቤት አከራዬ የጋሽ ጣሰው አገር የምትተከዪ የምትነቀዬ የዘመቻ ድንኳን
ብጉርና ችግር ከአባቴ ወርሼ ብኖርብሽ እንኳን
የማልቀያምሽ ሁሌ የማልምሽ
ኦ ማይ ጎድ ይመስገን እኔ እንዳለሁ አለው
ግማሽ እሩዝና ግማሽ ጤፍ በልቼ
አዋጅ እና ዜና ከአደባባይ ሳይሆን ከአይፎኔ ሰምቼ
ሀሜት ሲናፍቀኝ በስካይፒ አምቼ
ጥቃት ሲሰማኝ ፊስቡክ ላይ ሸፍቼ
በኮመንት እሩምታ ጠላቴን ደፍቼ
እኔ እንዳለው አለው
እንደምነሽ ሸገር እንደምነሽ ሸገር
የማይበገረው ወር እየጠበቀ የሚያገራግረው
የቤት አከራዬ የጋሽ ጣሰው አገር
የከሰመው ወንዝሽ የሚታየው ነጥፎ
እንደምነው ጣፎ እንዴት ነው ቀበና
እስቲ ድንጋይ ላጥምድ መረብ ልጣልና
ልክ እንደነ ፓሪስ እንደለንደን ሁላ
ፋፋቴም ባይኖርሽ ሽቅብ የሚፈላ
ምንጭሽ ከማን ያንሳል
ከፈነዳ ትቦ የወጣ ሰገራ ሰንጥቆሽ ይፈሳል
እንደምነሽ ሸገር የቅጠላቅጠል የፍራፍሬ አገር
አንድ ዘለላ ሙዝ ልጠሽ ባታበይኝ
በሙዝ ልጣች ጠልፈሽ የምታከባልይኝ
አሳድገሽኛል አሳድገሽኛል በማርና ወተት
የተሞላ ተረት እየተረክሽልኝ
ጥማቴን በጥማት እያረካሽልኝ
እንደምነሽ ሸገር ኦ ማይ ጎድ ይመስገን
እኔ እንዳለው አለው ሰርቼ ቀፍዬ
ሲነጋ ቀፍዬ ሲመሽም ከፍዬ
ስጋ ምታወፍር ነብስ የምታሳሳ
ዘናጭ አልጋ ሰታ እንቅልፍ የምትነሳ
አገር ላይ ተጥዬ
#Re #post
‹‹ ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ ፀሃይና ጨረቃን ተመልከት፡፡ ሁለቱንም ማወዳደር አትችልም፡፡ ምክንያቱም ሁለቱም በየጊዜያቸው ዓለምን ያበራሉና፡፡ ››
የእኔ፣ የአንተ፣ የእሱ፣ የእሷ እና የሁላችንም የሕይወት ፍሠት፣ የደስታ ስኬት፣ የኑሮ ተዳፋት፣ እጣ ፋንታ እና ዕድል አንድ አይደለም፡፡ እንደየተፈጥሯችን፣ እንደየመልካችን፣ እንደየአስተሳሰባችን፣ እንደየፍላጎታችን፣ እንደየስጦታችን፣ እንደየአካሄዳችን፣ እንደአጠቃቀማችን ሁለነገራችን፣ ዕጣ ፋንታችን፣ ዕድል ገጠመኛችን ፍፁም የተለያየ ነው፡፡ ከአንድ እናት የወጡ መንታ ልጆች እንኳን ስኬታቸውም ሆነ ውድቀታቸው ይለያያል፡፡ ስለዚህ ራስን ከሌሎች ጋር ማወዳደር አይቻልም፡፡
ለአንዳንዱ በቀለም ትምህርት በሕይወቱ ስኬትን ለመጎናፀፍ ይቀለዋል፡፡ ለሌላው ደሞ ዳገት ይሆንበታል፡፡ ለእከሌ ንግድ የሚሳካለት ሲሆን ለእንቶኔ ደሞ ንግድ ኪሳራ በኪሳራ ያደርጋታል፡፡ ይሄ ማለት ግን በጥረትና በልፋት ነገሮችን ማሳካት አይቻልም ማለት አይደለም፡፡ በልፋትና በጥረት የሚሳካላቸው ሠዎች እንዳሉ ሁሉ የማይሳካለቸውም እልፍ ናቸው፡፡ ስንት ዓመት ለፍተው ፍሬውን ሊያዩ ትንሽ ሲቀራቸው ገደ-ቢስ ሆነው ልፋታቸው መና የቀረ ጥቂቶች አይደሉም፡፡
ለዚህ ጥሩ ምሣሌ የሚሆነው የጨረቃና የፀሃይን ተፈጥሮ ማየት ነው፡፡ አንዱን ካንዱ ማበላለጥ አይቻልም፡፡ ጨረቃን ከፀሃይ ብናሳንስ በድቅድቅ ጨለማ የምታበራውን ብርሃን መካድ ይሆናል፡፡ ጨረቃንም ከፀሃይ ብናስበልጥ የፀሃይን ውለታ አይቶ እንዳላየ ማለፍ ነው የሚሆነው፡፡ ሁለቱም በየራሳቸው ጠቃሚዎቻችን ናቸው፡፡ ሠውን ከሠው ማሳነስም ሆነ ማበላለጥ የተገባ አይደለም፡፡ ሁሉም ሠው ለሃገሩም ሆነ ለዓለም የሚታይና የማይታይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ አለውና፡፡ ምንም እንኳን ታዋቂ ሠዎች ቢሞገሱም በነሱ ስር ግን ብዙ ተራ ሠዎች ለእነሱ እውቅና የድርሻቸውን አዋጥተዋል፡፡ ለዚች ዓለም በየትኛውም ደረጃ ያለ ሠው አስፈላጊ ነው፡፡ አምላክ የሠው ልጅን ወዶና ፈቅዶ ነው የፈጠረው፡፡ በመሆኑም ሁሉም የራሱን አሻራ ጥሎ ያልፋል፡፡
ስለዚህ አበበን ከከበደ ማወዳደር አይቻልም፡፡ አበበም የሚበረታበት ነገር እንዳለው ሁሉ ከበደም የራሱ ጠንካራ ጎን አለው፡፡ በርግጥ ከበደ የሚደክምበትን አበበ ሊበረታበት ይችል ይሆናል፡፡ ይሄ ደሞ ከበደ ከአበበ ያነሠ ነው ማለት አይደለም፡፡ ከበደም በራሱ አቅምና ተፈጥሮ ብርታቱን የሚያሳይበትና የሚነሳበት ጊዜ አለውና፡፡
‹‹ለሁሉም ጊዜ አለው›› እንዳለው ጠቢቡ ሠለሞን እከሌ በስኬት ፏ ብሎ እኔ እስካሁን እዛው ነኝ ብለህ አትዘን፡፡ አንተም ጠንክረህ ከሠራህ ኑሮህን ታበራ ዘንድ ስኬት ካንተ ጎን የሚቆምበት ጊዜ ሩቅ አይደለም፡፡ ዋናው ነገር በስራ እየተጉ ጊዜውን በትዕግስት መጠባበቅ ብቻ ነው፡፡
💚መልካም 💛ቀን ለሁላችን❤️
‹‹ ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ ፀሃይና ጨረቃን ተመልከት፡፡ ሁለቱንም ማወዳደር አትችልም፡፡ ምክንያቱም ሁለቱም በየጊዜያቸው ዓለምን ያበራሉና፡፡ ››
የእኔ፣ የአንተ፣ የእሱ፣ የእሷ እና የሁላችንም የሕይወት ፍሠት፣ የደስታ ስኬት፣ የኑሮ ተዳፋት፣ እጣ ፋንታ እና ዕድል አንድ አይደለም፡፡ እንደየተፈጥሯችን፣ እንደየመልካችን፣ እንደየአስተሳሰባችን፣ እንደየፍላጎታችን፣ እንደየስጦታችን፣ እንደየአካሄዳችን፣ እንደአጠቃቀማችን ሁለነገራችን፣ ዕጣ ፋንታችን፣ ዕድል ገጠመኛችን ፍፁም የተለያየ ነው፡፡ ከአንድ እናት የወጡ መንታ ልጆች እንኳን ስኬታቸውም ሆነ ውድቀታቸው ይለያያል፡፡ ስለዚህ ራስን ከሌሎች ጋር ማወዳደር አይቻልም፡፡
ለአንዳንዱ በቀለም ትምህርት በሕይወቱ ስኬትን ለመጎናፀፍ ይቀለዋል፡፡ ለሌላው ደሞ ዳገት ይሆንበታል፡፡ ለእከሌ ንግድ የሚሳካለት ሲሆን ለእንቶኔ ደሞ ንግድ ኪሳራ በኪሳራ ያደርጋታል፡፡ ይሄ ማለት ግን በጥረትና በልፋት ነገሮችን ማሳካት አይቻልም ማለት አይደለም፡፡ በልፋትና በጥረት የሚሳካላቸው ሠዎች እንዳሉ ሁሉ የማይሳካለቸውም እልፍ ናቸው፡፡ ስንት ዓመት ለፍተው ፍሬውን ሊያዩ ትንሽ ሲቀራቸው ገደ-ቢስ ሆነው ልፋታቸው መና የቀረ ጥቂቶች አይደሉም፡፡
ለዚህ ጥሩ ምሣሌ የሚሆነው የጨረቃና የፀሃይን ተፈጥሮ ማየት ነው፡፡ አንዱን ካንዱ ማበላለጥ አይቻልም፡፡ ጨረቃን ከፀሃይ ብናሳንስ በድቅድቅ ጨለማ የምታበራውን ብርሃን መካድ ይሆናል፡፡ ጨረቃንም ከፀሃይ ብናስበልጥ የፀሃይን ውለታ አይቶ እንዳላየ ማለፍ ነው የሚሆነው፡፡ ሁለቱም በየራሳቸው ጠቃሚዎቻችን ናቸው፡፡ ሠውን ከሠው ማሳነስም ሆነ ማበላለጥ የተገባ አይደለም፡፡ ሁሉም ሠው ለሃገሩም ሆነ ለዓለም የሚታይና የማይታይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ አለውና፡፡ ምንም እንኳን ታዋቂ ሠዎች ቢሞገሱም በነሱ ስር ግን ብዙ ተራ ሠዎች ለእነሱ እውቅና የድርሻቸውን አዋጥተዋል፡፡ ለዚች ዓለም በየትኛውም ደረጃ ያለ ሠው አስፈላጊ ነው፡፡ አምላክ የሠው ልጅን ወዶና ፈቅዶ ነው የፈጠረው፡፡ በመሆኑም ሁሉም የራሱን አሻራ ጥሎ ያልፋል፡፡
ስለዚህ አበበን ከከበደ ማወዳደር አይቻልም፡፡ አበበም የሚበረታበት ነገር እንዳለው ሁሉ ከበደም የራሱ ጠንካራ ጎን አለው፡፡ በርግጥ ከበደ የሚደክምበትን አበበ ሊበረታበት ይችል ይሆናል፡፡ ይሄ ደሞ ከበደ ከአበበ ያነሠ ነው ማለት አይደለም፡፡ ከበደም በራሱ አቅምና ተፈጥሮ ብርታቱን የሚያሳይበትና የሚነሳበት ጊዜ አለውና፡፡
‹‹ለሁሉም ጊዜ አለው›› እንዳለው ጠቢቡ ሠለሞን እከሌ በስኬት ፏ ብሎ እኔ እስካሁን እዛው ነኝ ብለህ አትዘን፡፡ አንተም ጠንክረህ ከሠራህ ኑሮህን ታበራ ዘንድ ስኬት ካንተ ጎን የሚቆምበት ጊዜ ሩቅ አይደለም፡፡ ዋናው ነገር በስራ እየተጉ ጊዜውን በትዕግስት መጠባበቅ ብቻ ነው፡፡
💚መልካም 💛ቀን ለሁላችን❤️
👍3
#እኔ #እምፈልገው
እውነት ለመናገር እኔ ምፈልገው
ካንቺ ጋር መጋባት
ይህን ሀምሌ ፊቴን : ደጋግሞ ማራባት
ከወፎች ጋር መንቃት : በጊዜ ቤት መግባት::
"ምንም ደሃ ቢሆን: ባይኖረውም ሀብት
ከደጃፍ ሲቀመጥ: ደስ ይላል አባት"
ለሚል መናኛ ጥቅስ: ኑሮየ ማይመጥን
ሲሻኝ በየባንኩ: ስፈልግ በሳጥን
የተረፈኝ ገንዘብ
ደጃፍ ላይ ቁጭ ብየ: ድሀ የምታዘብ
ተምሳሌትነቴ የሚዳረስ ባለም
ሞዴል አባወራ ተብየ ምሸለም
አገሬን ማስከበር
ህዝቤን ማስተባበር
የልጅ ልጅ አፍርቼ
በመቶ አመት ሙቼ
ስላሴ መቀበር
ምኞቴ ይህ ነበር::
እውነት ለመናገር እኔ እምፈልገው
ወንደላጤ ኑሮ
በሴቶች መታጀብ : ልክ እንዳውራ ዶሮ
ጊዜ ጥሎኝ ቢሄድ : ቀን ቢገሰግስም
መላው ጭንቅላቴ : ገብስማ ቢለብስም
ላቅማዳም ነው እንጂ: ለትዳር አልደርስም::
ደሞ
ዘር መዝራት እርሜ ነው : ደጋግሜ ባርስም
ባለመኖር ላሉት: ስቃይ አላወርስም
ቢፈልግ ሌላው ህዝብ
ይፈልፍል እንደዝንብ
ይባዛ እንደንጉዳይ
አገር ስራው ያውጣው! ሰው የራሱ ጉዳይ!!
የራሴ ፈጣሪ- ነኝ የራሴ ገዳይ!!
እኔ እምፈልገው...
እኔ እምፈልገው..
እኔ እምፈልገው
-----------
ገንዘብ ቢመዘበር: በገንዘብ ይተካል
እድሜ ለጉልበትሽ : በላቡ ለሚያድር
በውርስ በስጦታ : ግፋ ቢል በብድር::
በቆጠብነው ቁጥር
ጊዜ ነው የሚያጥር
እድሜ ነው የሚያልቀው
የምንፈልገውን በቅጡ ሳናውቀው::
👉በውቀቱ ስዩም
እውነት ለመናገር እኔ ምፈልገው
ካንቺ ጋር መጋባት
ይህን ሀምሌ ፊቴን : ደጋግሞ ማራባት
ከወፎች ጋር መንቃት : በጊዜ ቤት መግባት::
"ምንም ደሃ ቢሆን: ባይኖረውም ሀብት
ከደጃፍ ሲቀመጥ: ደስ ይላል አባት"
ለሚል መናኛ ጥቅስ: ኑሮየ ማይመጥን
ሲሻኝ በየባንኩ: ስፈልግ በሳጥን
የተረፈኝ ገንዘብ
ደጃፍ ላይ ቁጭ ብየ: ድሀ የምታዘብ
ተምሳሌትነቴ የሚዳረስ ባለም
ሞዴል አባወራ ተብየ ምሸለም
አገሬን ማስከበር
ህዝቤን ማስተባበር
የልጅ ልጅ አፍርቼ
በመቶ አመት ሙቼ
ስላሴ መቀበር
ምኞቴ ይህ ነበር::
እውነት ለመናገር እኔ እምፈልገው
ወንደላጤ ኑሮ
በሴቶች መታጀብ : ልክ እንዳውራ ዶሮ
ጊዜ ጥሎኝ ቢሄድ : ቀን ቢገሰግስም
መላው ጭንቅላቴ : ገብስማ ቢለብስም
ላቅማዳም ነው እንጂ: ለትዳር አልደርስም::
ደሞ
ዘር መዝራት እርሜ ነው : ደጋግሜ ባርስም
ባለመኖር ላሉት: ስቃይ አላወርስም
ቢፈልግ ሌላው ህዝብ
ይፈልፍል እንደዝንብ
ይባዛ እንደንጉዳይ
አገር ስራው ያውጣው! ሰው የራሱ ጉዳይ!!
የራሴ ፈጣሪ- ነኝ የራሴ ገዳይ!!
እኔ እምፈልገው...
እኔ እምፈልገው..
እኔ እምፈልገው
-----------
ገንዘብ ቢመዘበር: በገንዘብ ይተካል
እድሜ ለጉልበትሽ : በላቡ ለሚያድር
በውርስ በስጦታ : ግፋ ቢል በብድር::
በቆጠብነው ቁጥር
ጊዜ ነው የሚያጥር
እድሜ ነው የሚያልቀው
የምንፈልገውን በቅጡ ሳናውቀው::
👉በውቀቱ ስዩም
👍1
📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚
ውድ የቻናላችን ተከታታዮች በዘነበ ወላ የተፃፈውን ልጅነት የተሰኘውን መፅሐፍ ያላነበበው ካለ ሙሉውን በPdf ቀርቦላችኋል መልካም ንባብ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ውድ የቻናላችን ተከታታዮች በዘነበ ወላ የተፃፈውን ልጅነት የተሰኘውን መፅሐፍ ያላነበበው ካለ ሙሉውን በPdf ቀርቦላችኋል መልካም ንባብ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
💦 ከልጅነት ፍቅር አንዲት ጠብታ💦
በሰላላው መንገድ የትየለሌ እግር እንደ ሊጥ ባቦካው
ጸአዳ ጣትሽን ጉድፍ እንዳይነካው
ማጡን እየዘለልሽ
ዳጥ ዳጡን እያለፍሽ
ጤዛ የወረረው ዛፍ እየተደገፍሽ
ትንሽ ስትመጪ ብዙ ስታዘግሚ
ሁለቴ ተራምደሽ አስሪ ስትቆሚ
የተላከ ህፃን አስቁመሽ ስትስሚ
እኔ ስናፍቅሽ
እኔ ስጠብቅሽ
እንደ ጉድ ተውቤ ላማልልሽ ጥሬ
በጆትራ ዘይቤ ፀጉሬን አበጥሬ
ጅማት እያጠበኩ ጅማት እያላላሁ
የገዛ ከንፈሬን ቀርጥፌ እየበላሁ
ስጠብቅሽ በጣም
ምስልሽ ነው እንጂ አካልሽ አልመጣም
ባይኖቼ ስፈልግ መስኮት እከፍትና
ሌላ ነው የሚያልፈው በሰፊው ጎዳና
ያው ገጣባ አህያ ያቻት ድኩም በቅሎ
በግ እየጎተተ አለፈ ቆለኛ
ቅርጫት ያጎበጣት ሚስቱን አስከትሎ
ያውና ደሀ አደግ መንገድ ዳር የተኛ
የተጎነ ጎነ የሳር አንባ መስሎ
ባይኖቼ ሳማትር መስኮት እከፍትና
ሌላ ነው የሚያልፈው በሰፊው ጎዳና
ሁሉም ተለውጦ ያ ገጣባ አህያ ፀጉር አቆጥቁጦ
ያቺ ድኩም በቅሎ ሰጋር ፈረስ ቀድማ
ቆለኛው ሰውዬ ሙክት በጉን ሽጦ ለሚስቱ ነጭ ሻሽ ለሱ ሸራ ጫማ በትርፉ ሸምቶ
ሀሉም ከሄደበት ቀንቶት ተመልሶ
ሁሉም ከድቀቱ በወግ ተፈውሶ
እኔ ብቻ ቀረሁ
መንገድሽ እረዝሞ ባሳብ እያሳጠርኩ
አንቺን እየናፋኩ
አንቺን አየጠበኩ
ጅማት አያላላሁ ጅማት እያጠበኩ
፨በውቀቱ ስዩም፨
በሰላላው መንገድ የትየለሌ እግር እንደ ሊጥ ባቦካው
ጸአዳ ጣትሽን ጉድፍ እንዳይነካው
ማጡን እየዘለልሽ
ዳጥ ዳጡን እያለፍሽ
ጤዛ የወረረው ዛፍ እየተደገፍሽ
ትንሽ ስትመጪ ብዙ ስታዘግሚ
ሁለቴ ተራምደሽ አስሪ ስትቆሚ
የተላከ ህፃን አስቁመሽ ስትስሚ
እኔ ስናፍቅሽ
እኔ ስጠብቅሽ
እንደ ጉድ ተውቤ ላማልልሽ ጥሬ
በጆትራ ዘይቤ ፀጉሬን አበጥሬ
ጅማት እያጠበኩ ጅማት እያላላሁ
የገዛ ከንፈሬን ቀርጥፌ እየበላሁ
ስጠብቅሽ በጣም
ምስልሽ ነው እንጂ አካልሽ አልመጣም
ባይኖቼ ስፈልግ መስኮት እከፍትና
ሌላ ነው የሚያልፈው በሰፊው ጎዳና
ያው ገጣባ አህያ ያቻት ድኩም በቅሎ
በግ እየጎተተ አለፈ ቆለኛ
ቅርጫት ያጎበጣት ሚስቱን አስከትሎ
ያውና ደሀ አደግ መንገድ ዳር የተኛ
የተጎነ ጎነ የሳር አንባ መስሎ
ባይኖቼ ሳማትር መስኮት እከፍትና
ሌላ ነው የሚያልፈው በሰፊው ጎዳና
ሁሉም ተለውጦ ያ ገጣባ አህያ ፀጉር አቆጥቁጦ
ያቺ ድኩም በቅሎ ሰጋር ፈረስ ቀድማ
ቆለኛው ሰውዬ ሙክት በጉን ሽጦ ለሚስቱ ነጭ ሻሽ ለሱ ሸራ ጫማ በትርፉ ሸምቶ
ሀሉም ከሄደበት ቀንቶት ተመልሶ
ሁሉም ከድቀቱ በወግ ተፈውሶ
እኔ ብቻ ቀረሁ
መንገድሽ እረዝሞ ባሳብ እያሳጠርኩ
አንቺን እየናፋኩ
አንቺን አየጠበኩ
ጅማት አያላላሁ ጅማት እያጠበኩ
፨በውቀቱ ስዩም፨
👍1