#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
:
✍ድርሰት በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ኩማንደር መሀሪ ቀለም ወርቅን የመበቀል እቅዱ ከከሸፈበት በኋላ ሌላ እቅድ ወጥኖ ከነበረበት ቦታ ለውጥ አድርጎ ነው ከወራት መሰወር ቡኃላ ነው ሻሸመኔ ላይ ብቅ ያለው፡፡፡ዲላ ከተማ በሚኖርበት ወቅት በዙሪያው ባሉ የቅርብ ሰዎች የጠለቀች ፀሀዩ እዚህ ሻሸመኔ ላይ ድንገት ወጥታለች..በርታለች፡፡
በፊት በሚሰራው ተመሳሳይ ስራ የፖሊስ መኮንን ሆኖ ለዛውም የከተማዋ ፖሊስ አዛዥ ሆኖ ሻሸመኔ ላይ ብቅ ካለ ወራቶች ተቆጥረዋል፡፡ መሀሪ በዚህ ወቅት በከተማዋ ኑዋሪዎች ቅፅበታዊ በሚባል ሁኔታ ስሙ ገኗል፡፡ዕውቅናውን ላየ ሰው ወራቶች ብቻ የኖረ ሳይሆን ስድስት ዓመት ያሳለፈ ነው የሚመስለው፡
በከተማዋ ያተጐናጸፈው ዕውቅና ሶስት ገፅታዎች አሉት ፡፡አንደኛ ዘወትር የተቋጠረ እና የጨለመ ፊቱ…. ሁለተኛው ወሰን አልባ ጉበኝነቱ… እናም ሶስተኛው ለሰው ልጅ ያለው ንቀት እና ጭካኔ ናቸው፡፡ ከሶስቱ መካከል ግን ጉበኝነቱ ቀደምትነቱን ይይዛል፡፡እርግጥ በኢትዬጰያ ለተንሰራፋው ስር የሰደደ ሙስኝነት የሻሸመኔ ከተማ በተለይ ከኮንትሮባንድ ጋር ተያይዞ ዋናዋ መገለጫ እና እንደ ናሙና የምትጠቀስ እንደመሆኗ መጠን እሱ ብቻ ሳይሆን መላ ባለስልጣኖች በሚያስብል ደረጃ ተክነውበታል፡፡ለዚህ መነሻ ምክንያቱም ምን አልባት ከተማዋ በንግድ እንቅስቃሴዋ በጣም የሞቀች እና የደመቀች በመሆኗ እና ከአምስት የሚበልጡ ዋና ዋና በሮች ያሏትና እሱን ተከትሎ ብዙ ሺ ሰዎች በየዕለቱ ለጉዳይ ገብተው የሚወጡባት የንግድ መዲናና ረብጣ ብር ከአንዱ ግለሰብ ወደሌላው ግለሰብ የሚሽከረከርባት ከተማ ስለሆነች ሊሆን ይችላል ብለን የራሳችንን መላ ምት ብንወስድ ብዙም አንሳሳትም፤ኩማደር መሀሪ ከወራቶች መሰወር ቡኃላ ሻሸመኔ ላይ ብቅ ያለው ግን ይሄንን አገናዝቦ ወይም የሚሰበስበው ጉቦ ዓላማው አድርጐ አልነበረም ፡፡ዋና ምክንያቱ ቀለም ወርቅ ነው፡፡ለእናቱ ህይወት እልፈት ምክንያት የሆነው የቀድሞ የእንጀራ አባቱ ቀለም ወርቅ ከገባበት እስር ቤት በገንዘብ ሀይል ወቶ አዲስ ቤት መስርቶ፤ አዲስ ሚስት አግብቶ እዚህ ሻሸመኔ ስለሚኖር ነው፡፡በቀሉን ለሁለተኛ ጊዜ ለማራመድ እንዲቀለው ስለወሰነ ነው፡፡
የሚገርመው ልክ እሱ ሻሸመኔ ከተማ በከተመበት ተመሳሳይ ወቅት ሌላ ተፅዕኖ ፈጣሪ እንግዳ ሰው በከተማዋ ተከስቷል፡፡አባ ሽፍንፍን ይባላሉ፡፡መቼስ ይህቺ ዓለም ሁል ጊዜ በተቃራኒ ኩነቶች የተወጠርች ነች..ያም ነው ሚዛኗን ጠብቃ እንድትቀጥል ያስቻላት፡፡ችግር እና ድሎት…ጨለማና ብርሀን…ክፋትና ደግነት…በቀል እና ይቅር ባይነት ወዘተ ወዲህና ወዲያ ወጥረው ያቆሟታል ፡፡እናም እኚ አባ ሽፍንፍን የኩማደር መሀሪ የበቀል መጋኛ አጠናግሮ የሚያተራምሳትን ከተማ እሷቸው ደግሞ በደግነት እና በቸርነት ቀዝቀዝ ያደርጓታል፡፡እሱ ያቀጣጠለውን የክፋት እሳት እሷቸው በበጐነት ፀበል ያዳፍኑታል፡፡
እኚ አባ ሽፍንፍን የተባሉት ቄስ ትክክለኛ ስማቸው ሌላ ነው ፡፡አባ ሽፍንፍን የተባሉት ከአለባበሳቸው በመነሳት ነው፡፡እግር ጠፍራቸው ሚደርስ ጥቁር ቀሚስ ለብሰው ፊታቸውን ሙሉ በሙሉ ዓይኖቻቸውን ብቻ አስቀርተው በሻርባቸው ይጠቀለሉና በላዩ ላይ ጥቁር የመነኩሴ ቆብ ይደፉበታል፡፡በዛም አያበቁም የተቀረችውን ለእይታ የተጋለጠች ዓይኖቻቸው አካባቢ የቀረችውን የሰውነታውን ክፍል በግዙፍ ጥቁር መነጽር ይጋርዱታል፡፡በቃ ከእሷቸው አካላት በግልጽ የሚታዩት መስቀል የሚጨብጡት የእጆቻቸው ጣቶች ብቻ ናቸው፡፡ከየት እንደመጡ ….?እንዲህ ዓይነት አለባበስ ለምን እንደሚለብሱ…. ?በፊት የት ይኖሩ እንደነበረ… ?ከመላ ምት በስተቀር ማንም በእርግጠኝነት የሚያውቅ የለም፡፡ግን የሚገርመው ሻሸመኔ መኖር በጀመሩ በወራቶችጊዜ ውስጥ የኩማደር መሀሪን ያህል ዝናን ታዋቂነትን ተጐናጽፈዋል፡፡ የእውቅናቸው መስመር ግን ለየቅል ነው..
እሷቸው የተቸገረውን ረድተው...የታረዘውን አልብሰው..የተራበውን አጉርሰው ያገኙት ዝና ነው፡፡እኚ ቄስ የገቢ ምንጫቸው ምን እንደሆነ አይታወቅም፤ ግን በርከት ያለ ብር የባንክ ደብተራቸው ውስጥ አለ፡፡አንዳንድ እናውቃለን የሚሉ ሰዎች ሲያንሾካሹኩ እንደተሰማው እኚ አባ ሽፍንፍን የተባሉ ቄስ አሜሪካ ሀገር ብዙ አመት ኖረው ጠርቀም ያለ ጥሪት አጠራቅመው ቀሪ ህይወታቸውን ቅድስት ሀገር የሚል መንፈሳዊ ስም ወደተጐናፀፈች ሀገራቸው ተመልሰው የቅድስና ስራ እየሰሩ ለማሳለፍ ወስነው እንደመጡ የሚናገሩ ግለሰቦች አሉ..የተረጋገጠ ባይሆንም
ሌላው ገራሚው ነገር ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ ኩማንደር መሀሪ እና እኚህ አባ ሽፍንፍን የተባሉ ቄስ አንድ ግዙፍ በለአንድ ፎቅ ቪላ በጋራ ተጋርተው ይኖራሉ ፡፡ እሳቸው በምድር ቤቱ ውስጥ ባሉ ክፍሎች ሲኖሩ እሱ ደግማ በላይኛው ወለል ባሉ ክፍሎች ይኖራል፡፡ግን ይህ ቤት በሁለት ግቢ ተከፍሎል እሱ ሚጠቀመው የፊት ለፊቱን ግቢ ሲሆን እሳቸው ደግሞ የጀርባውን ግቢና ነው፡፡ኩማደር መሀሪ ሻሸመኔ የከተመው ለበቀል ነው፡፡እኚ ሚስጥራዊ ቄስ ሻሸመኔ ለምን ጉዳይ እንደተገኙ አይታወቅም..?
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ሁለቱም እናትና ልጅ ያለቅሳሉ…ከፊት ለፊታቸው የተቀመጠው ፖሊስ ይጠይቃቸዋል፡፡በደከመ አንደበት በተሰበረ ቃል ይመልሳሉ፡፡ሰዎቹ ሄለን እና አያቷ ናቸው፡፡ቦታው በከተማው ፖሊስ ጣቢያ ግቢ ውስጥ ነው ፡፡ተከሰው አይደለም የቀረቡት..ለመክሰስ ነው፡፡ ማያውቁትን ጠላታቸውን ለመክሰስ..
‹‹እስቲ ትዕይንቱን ከመጀመሪያው አንስተው አስረዱኝ?›› ፖሊሱ በፖሊሳዊ ግርማ ሞገሱ እንደተኮፈሰ የመጀመሪያ ጥያቄውን ሰነዘረ አሮጊቶ የተሸበሸበ ፊታቸውን ላይ ኮለል እያለ የሚወርደውን እንባቸውን በተጨማደደ እና በቆረፈደ እጃቸው ጠረግ ጠረግ በማድረግ መናገር ጀመሩ ‹‹ከትናንት ወዲያ ነው በቀኑ ኤሌክትሪክ ተቋረጠብን ..ከሰፈሩ የእኛ ቤት ብቻ ነው ተነጥሎ የተቋረጠብን፡፡ መብራት ኃይል አመለከትን …ቆይ ይቀጠልላችኃል አሉን እና ግን ሳይመጡ ዋሉ፡፡ ሲመሽ ያው ትልቁን ቤት ገርበብ አድርገን ኩሽና ሄደን በእንጨት ቡና አፍልተን ከልጄ ጋ ከጠጣን ቡሃላ ወደ ቤታችን በመግባን እራችንን ቀድመን በልተን ስለነበረ በጨለማው ዳበሳ ወደ መኝታችን ነበር ያመራነው፡፡ ሀገር አማን ነው ብለን የተለመደ እንቅልፋችንን ከተኛን ቡኃላ ባልታሰበ ሁኔታ ለሊት ላይ እላያችን ላይ ባትሪ በራብን ፡፡ ባነን ስናስተውላቸው ሁለት ጐረምሶች ናቸው፡፡
አንዱ ልጄ ላይ አንደኛው እኔ ላይ ሽጉጥ ደቅነው ነበር፡፡ ከፍራቻችን አንጻር መተንፈስ እንኳን አልቻልንም ..ወዲያው አንደኛው በጐረነነ ድምጽ ልብሳችንን በአስቸኳይ እንድንለብስ አዘዘን..በዛ በጨለማ በመርበትበት ሁለታችንም ያለውን ፈጸምን፡፡እኔ አቅሜን አውቄ አልተፍጨረጨርኩም ብቻ ለልጄ እፀልይ ነበር..::ጌታዬ በእስተእርጅና እንዳያሳቅቀኝ ..በዛ ጭንቅ ውስጥ እንኳን መማፀኔን አላቆምኩም፡፡ከዛ ቡኃላ ልጄንም እኔንም በገመድ እጆቻችንን ወደ ኃላ ጠፈሩን::ዓይኖቻንን በፍርሀት ከማቁለጭለጭ ውጭ ምንም ማድረግ አልቻልንም፡፡አንደኛው ሽጉጥ እንደደቀነ እኛን ሲጠብቀን ሌለኛው ወደ ውጭ ወጣና ባለ አስር ሊትሩን ጄሪካን ይዞ መጣ… ክዳኑን ከፈተና እቤት ውስጥ ማርከፍከፍ ጀመረ፡፡ መጀመሪያ ውሀ መስሎኝ ነበር ብኃላ ግን ምንነቱን በሽታው ወዲያው ተረዳውት ፣ጋዝ ነው..፡፡ጉዳችን ፈላ አልኩ፡፡…እመብርሀን ድረሺልን አልኩ ..በቁማችን እቤታችንን በላያችን ላይ ዘግተው ሊያነዱን ነው ስል አሰብኩ፡፡እኔ እንኳን በልቼያለውም፤ ኖሬያለውም ለጨቅላዋ ልጄ ሰጋው፡፡ቡኃለ ግን አርከፍክፎ
:
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
:
✍ድርሰት በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ኩማንደር መሀሪ ቀለም ወርቅን የመበቀል እቅዱ ከከሸፈበት በኋላ ሌላ እቅድ ወጥኖ ከነበረበት ቦታ ለውጥ አድርጎ ነው ከወራት መሰወር ቡኃላ ነው ሻሸመኔ ላይ ብቅ ያለው፡፡፡ዲላ ከተማ በሚኖርበት ወቅት በዙሪያው ባሉ የቅርብ ሰዎች የጠለቀች ፀሀዩ እዚህ ሻሸመኔ ላይ ድንገት ወጥታለች..በርታለች፡፡
በፊት በሚሰራው ተመሳሳይ ስራ የፖሊስ መኮንን ሆኖ ለዛውም የከተማዋ ፖሊስ አዛዥ ሆኖ ሻሸመኔ ላይ ብቅ ካለ ወራቶች ተቆጥረዋል፡፡ መሀሪ በዚህ ወቅት በከተማዋ ኑዋሪዎች ቅፅበታዊ በሚባል ሁኔታ ስሙ ገኗል፡፡ዕውቅናውን ላየ ሰው ወራቶች ብቻ የኖረ ሳይሆን ስድስት ዓመት ያሳለፈ ነው የሚመስለው፡
በከተማዋ ያተጐናጸፈው ዕውቅና ሶስት ገፅታዎች አሉት ፡፡አንደኛ ዘወትር የተቋጠረ እና የጨለመ ፊቱ…. ሁለተኛው ወሰን አልባ ጉበኝነቱ… እናም ሶስተኛው ለሰው ልጅ ያለው ንቀት እና ጭካኔ ናቸው፡፡ ከሶስቱ መካከል ግን ጉበኝነቱ ቀደምትነቱን ይይዛል፡፡እርግጥ በኢትዬጰያ ለተንሰራፋው ስር የሰደደ ሙስኝነት የሻሸመኔ ከተማ በተለይ ከኮንትሮባንድ ጋር ተያይዞ ዋናዋ መገለጫ እና እንደ ናሙና የምትጠቀስ እንደመሆኗ መጠን እሱ ብቻ ሳይሆን መላ ባለስልጣኖች በሚያስብል ደረጃ ተክነውበታል፡፡ለዚህ መነሻ ምክንያቱም ምን አልባት ከተማዋ በንግድ እንቅስቃሴዋ በጣም የሞቀች እና የደመቀች በመሆኗ እና ከአምስት የሚበልጡ ዋና ዋና በሮች ያሏትና እሱን ተከትሎ ብዙ ሺ ሰዎች በየዕለቱ ለጉዳይ ገብተው የሚወጡባት የንግድ መዲናና ረብጣ ብር ከአንዱ ግለሰብ ወደሌላው ግለሰብ የሚሽከረከርባት ከተማ ስለሆነች ሊሆን ይችላል ብለን የራሳችንን መላ ምት ብንወስድ ብዙም አንሳሳትም፤ኩማደር መሀሪ ከወራቶች መሰወር ቡኃላ ሻሸመኔ ላይ ብቅ ያለው ግን ይሄንን አገናዝቦ ወይም የሚሰበስበው ጉቦ ዓላማው አድርጐ አልነበረም ፡፡ዋና ምክንያቱ ቀለም ወርቅ ነው፡፡ለእናቱ ህይወት እልፈት ምክንያት የሆነው የቀድሞ የእንጀራ አባቱ ቀለም ወርቅ ከገባበት እስር ቤት በገንዘብ ሀይል ወቶ አዲስ ቤት መስርቶ፤ አዲስ ሚስት አግብቶ እዚህ ሻሸመኔ ስለሚኖር ነው፡፡በቀሉን ለሁለተኛ ጊዜ ለማራመድ እንዲቀለው ስለወሰነ ነው፡፡
የሚገርመው ልክ እሱ ሻሸመኔ ከተማ በከተመበት ተመሳሳይ ወቅት ሌላ ተፅዕኖ ፈጣሪ እንግዳ ሰው በከተማዋ ተከስቷል፡፡አባ ሽፍንፍን ይባላሉ፡፡መቼስ ይህቺ ዓለም ሁል ጊዜ በተቃራኒ ኩነቶች የተወጠርች ነች..ያም ነው ሚዛኗን ጠብቃ እንድትቀጥል ያስቻላት፡፡ችግር እና ድሎት…ጨለማና ብርሀን…ክፋትና ደግነት…በቀል እና ይቅር ባይነት ወዘተ ወዲህና ወዲያ ወጥረው ያቆሟታል ፡፡እናም እኚ አባ ሽፍንፍን የኩማደር መሀሪ የበቀል መጋኛ አጠናግሮ የሚያተራምሳትን ከተማ እሷቸው ደግሞ በደግነት እና በቸርነት ቀዝቀዝ ያደርጓታል፡፡እሱ ያቀጣጠለውን የክፋት እሳት እሷቸው በበጐነት ፀበል ያዳፍኑታል፡፡
እኚ አባ ሽፍንፍን የተባሉት ቄስ ትክክለኛ ስማቸው ሌላ ነው ፡፡አባ ሽፍንፍን የተባሉት ከአለባበሳቸው በመነሳት ነው፡፡እግር ጠፍራቸው ሚደርስ ጥቁር ቀሚስ ለብሰው ፊታቸውን ሙሉ በሙሉ ዓይኖቻቸውን ብቻ አስቀርተው በሻርባቸው ይጠቀለሉና በላዩ ላይ ጥቁር የመነኩሴ ቆብ ይደፉበታል፡፡በዛም አያበቁም የተቀረችውን ለእይታ የተጋለጠች ዓይኖቻቸው አካባቢ የቀረችውን የሰውነታውን ክፍል በግዙፍ ጥቁር መነጽር ይጋርዱታል፡፡በቃ ከእሷቸው አካላት በግልጽ የሚታዩት መስቀል የሚጨብጡት የእጆቻቸው ጣቶች ብቻ ናቸው፡፡ከየት እንደመጡ ….?እንዲህ ዓይነት አለባበስ ለምን እንደሚለብሱ…. ?በፊት የት ይኖሩ እንደነበረ… ?ከመላ ምት በስተቀር ማንም በእርግጠኝነት የሚያውቅ የለም፡፡ግን የሚገርመው ሻሸመኔ መኖር በጀመሩ በወራቶችጊዜ ውስጥ የኩማደር መሀሪን ያህል ዝናን ታዋቂነትን ተጐናጽፈዋል፡፡ የእውቅናቸው መስመር ግን ለየቅል ነው..
እሷቸው የተቸገረውን ረድተው...የታረዘውን አልብሰው..የተራበውን አጉርሰው ያገኙት ዝና ነው፡፡እኚ ቄስ የገቢ ምንጫቸው ምን እንደሆነ አይታወቅም፤ ግን በርከት ያለ ብር የባንክ ደብተራቸው ውስጥ አለ፡፡አንዳንድ እናውቃለን የሚሉ ሰዎች ሲያንሾካሹኩ እንደተሰማው እኚ አባ ሽፍንፍን የተባሉ ቄስ አሜሪካ ሀገር ብዙ አመት ኖረው ጠርቀም ያለ ጥሪት አጠራቅመው ቀሪ ህይወታቸውን ቅድስት ሀገር የሚል መንፈሳዊ ስም ወደተጐናፀፈች ሀገራቸው ተመልሰው የቅድስና ስራ እየሰሩ ለማሳለፍ ወስነው እንደመጡ የሚናገሩ ግለሰቦች አሉ..የተረጋገጠ ባይሆንም
ሌላው ገራሚው ነገር ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ ኩማንደር መሀሪ እና እኚህ አባ ሽፍንፍን የተባሉ ቄስ አንድ ግዙፍ በለአንድ ፎቅ ቪላ በጋራ ተጋርተው ይኖራሉ ፡፡ እሳቸው በምድር ቤቱ ውስጥ ባሉ ክፍሎች ሲኖሩ እሱ ደግማ በላይኛው ወለል ባሉ ክፍሎች ይኖራል፡፡ግን ይህ ቤት በሁለት ግቢ ተከፍሎል እሱ ሚጠቀመው የፊት ለፊቱን ግቢ ሲሆን እሳቸው ደግሞ የጀርባውን ግቢና ነው፡፡ኩማደር መሀሪ ሻሸመኔ የከተመው ለበቀል ነው፡፡እኚ ሚስጥራዊ ቄስ ሻሸመኔ ለምን ጉዳይ እንደተገኙ አይታወቅም..?
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ሁለቱም እናትና ልጅ ያለቅሳሉ…ከፊት ለፊታቸው የተቀመጠው ፖሊስ ይጠይቃቸዋል፡፡በደከመ አንደበት በተሰበረ ቃል ይመልሳሉ፡፡ሰዎቹ ሄለን እና አያቷ ናቸው፡፡ቦታው በከተማው ፖሊስ ጣቢያ ግቢ ውስጥ ነው ፡፡ተከሰው አይደለም የቀረቡት..ለመክሰስ ነው፡፡ ማያውቁትን ጠላታቸውን ለመክሰስ..
‹‹እስቲ ትዕይንቱን ከመጀመሪያው አንስተው አስረዱኝ?›› ፖሊሱ በፖሊሳዊ ግርማ ሞገሱ እንደተኮፈሰ የመጀመሪያ ጥያቄውን ሰነዘረ አሮጊቶ የተሸበሸበ ፊታቸውን ላይ ኮለል እያለ የሚወርደውን እንባቸውን በተጨማደደ እና በቆረፈደ እጃቸው ጠረግ ጠረግ በማድረግ መናገር ጀመሩ ‹‹ከትናንት ወዲያ ነው በቀኑ ኤሌክትሪክ ተቋረጠብን ..ከሰፈሩ የእኛ ቤት ብቻ ነው ተነጥሎ የተቋረጠብን፡፡ መብራት ኃይል አመለከትን …ቆይ ይቀጠልላችኃል አሉን እና ግን ሳይመጡ ዋሉ፡፡ ሲመሽ ያው ትልቁን ቤት ገርበብ አድርገን ኩሽና ሄደን በእንጨት ቡና አፍልተን ከልጄ ጋ ከጠጣን ቡሃላ ወደ ቤታችን በመግባን እራችንን ቀድመን በልተን ስለነበረ በጨለማው ዳበሳ ወደ መኝታችን ነበር ያመራነው፡፡ ሀገር አማን ነው ብለን የተለመደ እንቅልፋችንን ከተኛን ቡኃላ ባልታሰበ ሁኔታ ለሊት ላይ እላያችን ላይ ባትሪ በራብን ፡፡ ባነን ስናስተውላቸው ሁለት ጐረምሶች ናቸው፡፡
አንዱ ልጄ ላይ አንደኛው እኔ ላይ ሽጉጥ ደቅነው ነበር፡፡ ከፍራቻችን አንጻር መተንፈስ እንኳን አልቻልንም ..ወዲያው አንደኛው በጐረነነ ድምጽ ልብሳችንን በአስቸኳይ እንድንለብስ አዘዘን..በዛ በጨለማ በመርበትበት ሁለታችንም ያለውን ፈጸምን፡፡እኔ አቅሜን አውቄ አልተፍጨረጨርኩም ብቻ ለልጄ እፀልይ ነበር..::ጌታዬ በእስተእርጅና እንዳያሳቅቀኝ ..በዛ ጭንቅ ውስጥ እንኳን መማፀኔን አላቆምኩም፡፡ከዛ ቡኃላ ልጄንም እኔንም በገመድ እጆቻችንን ወደ ኃላ ጠፈሩን::ዓይኖቻንን በፍርሀት ከማቁለጭለጭ ውጭ ምንም ማድረግ አልቻልንም፡፡አንደኛው ሽጉጥ እንደደቀነ እኛን ሲጠብቀን ሌለኛው ወደ ውጭ ወጣና ባለ አስር ሊትሩን ጄሪካን ይዞ መጣ… ክዳኑን ከፈተና እቤት ውስጥ ማርከፍከፍ ጀመረ፡፡ መጀመሪያ ውሀ መስሎኝ ነበር ብኃላ ግን ምንነቱን በሽታው ወዲያው ተረዳውት ፣ጋዝ ነው..፡፡ጉዳችን ፈላ አልኩ፡፡…እመብርሀን ድረሺልን አልኩ ..በቁማችን እቤታችንን በላያችን ላይ ዘግተው ሊያነዱን ነው ስል አሰብኩ፡፡እኔ እንኳን በልቼያለውም፤ ኖሬያለውም ለጨቅላዋ ልጄ ሰጋው፡፡ቡኃለ ግን አርከፍክፎ
👍3
ሲጨርስ ሁለታችንንም እየገፈታሩ ከቤት አስወጡን፡፡ ተመስገን ነው … ቢያንስ ከቃጠሎ ተርፈናል..ከዛ ወደ ጎሮ ወሰዱን እና ግቢ ውስጥ ካለ ዛፍ ላይ ሁለታንንም አቆራኝተው አሰሩን፤ አፋችንን አሸጉት እና ጥለውን ወደ ትልቁ ቤት ተመለሱ፡፡ከዛ ግቢውን ለቀው ሲወጡ ተመለከትኩ..ግራ ገባኝ..እቤት ገብተው ምን አደረጉ? እራሴን ጠየቅኩ ..መልስ ላገኝ አልቻልኩም..ወደ ልጄ መልስ ለማግኘት ፊቴን ባዞር አፌ ለካ ታፍኖል ….ከዛ ቡኃላ ከቤታችን ውስጥ እሳት ሲንቀለቀል ነው የያነው..ምን እናድርግ ከእስራታችን ራሳችንን ለመላቀቅ አልተቻለንም...የጐረምሶቹ ጠንካራ እጅ የተበተበው ጠንካራ እስር ነበር...
ከትንሽ ደቂቃ ቡኃላ እሳቱ እየተንቀለቀለ ይወጣ ጀመር… ምን እናድርግ ?እንዳንጮኸ እና እርዳታ እንዲደርስልን እንዳንጠይቅ አፋችን ተለጉሞል ቡኃላ ቆርቆሮ እየተገነጠለ መብረር ጀመረ… ሁሉነገር በእሳቱ ተበልቶ ሊጠናቀቅ ሲል ጭሱን እና የሚንቀለቀለውን እሳት አይተው መሰለኝ ፖሊሶች ደረሱ፡፡ መሳሪያ ተተኮሰ ህዝቡ ተገልብጦ ወጣ… እኛንም ፈቱን ፡፡ ግን ከአመድ በስተቀር ምንም የተረፈልን ነገር የለም፡፡››
‹‹በጣም ይገርምል..በዚህ መጠን ይበቀለናል ብላችሁ የምታስቡት የተጣላችሁት ፤ ቂም ይዞብናል ብላችሁ የምትጠረጥሩት ሰው የለም?››
‹‹ኸረ በፍፁም ››መለሱ አሮጊቷ
‹‹አንቺስ እህት?›› አላት ወደ ሄለን አተኩሮ እየተመለከተ
‹‹ በየትኛውም መጠን ባበሳጨው ከጥፊ ባለፈ ይበቀለኛ ብዬ የማስበው ምንም አይነት ጠላት የለኝም፡፡ ሊኖረኝምም አይችልም…››
‹‹እሺ የሰዎቹን አካላዊ ቁመና ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?››
ሄለን መናገር ጀመረች‹‹ምንም አይለዩም ፡፡ሁለቱም ሰማያዊ ቱታ ለብሰው ጥቁር ጭንብል አጥልቀዋል፡፡ሁለቱም ግዙፍ አቋም ቢኖራቸውም አንደኛው ግን በተለየ መልኩ እንደከባድ ሻምፒዬን ቦክሰኛ ጡንቻው ፈረጣመ መሆኑ በግልጽ ያስታውቃል፡፡››
ፖሊሱ መጠየቅ አለብኝ ብሎ ያሰባቸውን ጥያቄዎች ጨርሶ ቃላቸውን ተቀብሎ ካጠናቀቀ ቡኃላ‹‹በሉ ክትትሉን በተቻለ መጠን በፍጥነት እናካሂዳለን..እርግጠኛ ነኝ የእነዚህ አውዳሚዎችን ዱካ በቅርብ ጊዜ ደርሰንበት ለፍርድ እናቀርባቸዋለን…››በማለት የማጠቃለያ ንግግር አደረገ እና ሊሸኛቸው ተከትሎቸው ወጣ ….በተከሰተው ነገር ከልቡ አዝኗልም ደንግጦልም..ምክንቱም እነዚህ ሰዎች ለሮዝ ቤተሰቦች ናቸው..ከሮዝ ጋ ደግሞ በሆነ አጋጣሚ አንሶላም ታሪክም ተጋርተዋል….ስለዚህ ጉዳዩን እንከአንጀቱ ነው ቃል የገባላቸው፡፡ ነገሩን በትኩረት ሊከታተለው..የምርመራውን ቡድን እራሱ ሊመራው…..
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
የፖሊስ ጣቢያውን በራፍ እንደወጡ አንድ ባለ አይጣማ ቀለም ቪታራ መኪና ፊት ለፊት ቆማ ተመለከቱ፡፡ ወዲው አንድ ቄስ ከውስጡ ወጡና ወደ እነሱ ማምራት ጀመሩ..የተለመደውን ሽፍንፍን አለባበስ የለበሱት አባ ሽፍንፍን ነበሩ..አጠገባቸው ሲደርሱ‹‹እቤት የተቃጠለባችሁ እናንተ ናችሁ?››ሲሉ በተረጋጋ እና በተጐተተ ንግግር ጠየቁ አባ ሽፍንፍን…
‹‹አዎ አባቴ..››አሉ አሮጊቷ ፈጠን ብለው
‹‹ስለ እናንተን ጉዳይ አንድ ወዳጄ ከዚህ ደውሎ ነግሮኝ ከሻሸመኔ ነው የመጣውት…አባ ኃይለ ጊርጊስ እባላለው››
ሶስቱም ደነገጡ…. በተለይ ፖሊሱ፡፡ስለ እኚህ ቄስ ዝና ብዙ ብዙ ሰምቷል..ሰምቶም በልቡ አድንቋቸው ነበር ..ሳይታሰብ ዛሬ በአጋጣሚ በአካል ሊያያቸው ስለቻለ ተደሰተ‹‹..ለምን ፊታቸውን ግልጽ አያደርጉትም? ››ሲል በውስጡ የተፈጠረውን ጥያቄ አብሰለሰለ
‹‹ኦ አባቴ እርሶ ኖት እንዴ ?ምን እንርዳዎት?››አለ ፖሊሱ
‹‹በጣም አመሰግናለው ኩማደር ፡፡አሁን ከሻሸመኔ የመጣውት እንዳልኩህ የእዚህን ቤተሰብ መጐዳት ሰምቼ ነው..እነሱን ፍለጋ ወደ ሰፈራቸው ሄጄ ጐረቤቶቻቸውን ስጠይቅ ወደ እዚህ እንዳመሩ ተነገረኝና ወደ እዚህ መጣው ፡፡ ትንሽ ከእነሱ ጋ ለማውራት ፈልጌያለው..ሁኔታዎች ተስተካክለው እቤታቸውን መልሰን ማሰራት እስክንችል ድረስ እኔ ጋ እንዲሆኑ እፈልጋለው….ወደ ሻሸመኔ ልወስዳቸው ነው፡፡ አንተ የምትፈልጋቸው ከሆነ መጥተህ ልታናግራቸው ወይም ደውለህ እንዲመጡ እና እንዲያናግሩህ ማድረግ ትችላለህ..ምን ይመስልሀል?፡፡››
‹‹ኸረ ጥሩ ሀሳብ ነው›› በደስታ ተስማማ
አባ ሽፍንፍን ኩማደሩን ተሰናበቱና ሄለን እና አያቷን ወደ መኪና ውስጥ እንዲገቡ ጋበዞቸው..ሁለቱም ግራ በመጋባ እና በመደነቅ ውስጥ እንዳሉ… ያለምንም መከራከር እግዚያብሄር ከገቡበት መከራ መዞ ሊያወጣቸው ፈልጎ ቄሱን ወደእነሱ እንደላከላቸው በማመን ያለምንም ማቅማማት በእሺታ ያሏቸውን አደረጉ…ጉዞ ወደሻሸመኔ …
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
ከትንሽ ደቂቃ ቡኃላ እሳቱ እየተንቀለቀለ ይወጣ ጀመር… ምን እናድርግ ?እንዳንጮኸ እና እርዳታ እንዲደርስልን እንዳንጠይቅ አፋችን ተለጉሞል ቡኃላ ቆርቆሮ እየተገነጠለ መብረር ጀመረ… ሁሉነገር በእሳቱ ተበልቶ ሊጠናቀቅ ሲል ጭሱን እና የሚንቀለቀለውን እሳት አይተው መሰለኝ ፖሊሶች ደረሱ፡፡ መሳሪያ ተተኮሰ ህዝቡ ተገልብጦ ወጣ… እኛንም ፈቱን ፡፡ ግን ከአመድ በስተቀር ምንም የተረፈልን ነገር የለም፡፡››
‹‹በጣም ይገርምል..በዚህ መጠን ይበቀለናል ብላችሁ የምታስቡት የተጣላችሁት ፤ ቂም ይዞብናል ብላችሁ የምትጠረጥሩት ሰው የለም?››
‹‹ኸረ በፍፁም ››መለሱ አሮጊቷ
‹‹አንቺስ እህት?›› አላት ወደ ሄለን አተኩሮ እየተመለከተ
‹‹ በየትኛውም መጠን ባበሳጨው ከጥፊ ባለፈ ይበቀለኛ ብዬ የማስበው ምንም አይነት ጠላት የለኝም፡፡ ሊኖረኝምም አይችልም…››
‹‹እሺ የሰዎቹን አካላዊ ቁመና ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?››
ሄለን መናገር ጀመረች‹‹ምንም አይለዩም ፡፡ሁለቱም ሰማያዊ ቱታ ለብሰው ጥቁር ጭንብል አጥልቀዋል፡፡ሁለቱም ግዙፍ አቋም ቢኖራቸውም አንደኛው ግን በተለየ መልኩ እንደከባድ ሻምፒዬን ቦክሰኛ ጡንቻው ፈረጣመ መሆኑ በግልጽ ያስታውቃል፡፡››
ፖሊሱ መጠየቅ አለብኝ ብሎ ያሰባቸውን ጥያቄዎች ጨርሶ ቃላቸውን ተቀብሎ ካጠናቀቀ ቡኃላ‹‹በሉ ክትትሉን በተቻለ መጠን በፍጥነት እናካሂዳለን..እርግጠኛ ነኝ የእነዚህ አውዳሚዎችን ዱካ በቅርብ ጊዜ ደርሰንበት ለፍርድ እናቀርባቸዋለን…››በማለት የማጠቃለያ ንግግር አደረገ እና ሊሸኛቸው ተከትሎቸው ወጣ ….በተከሰተው ነገር ከልቡ አዝኗልም ደንግጦልም..ምክንቱም እነዚህ ሰዎች ለሮዝ ቤተሰቦች ናቸው..ከሮዝ ጋ ደግሞ በሆነ አጋጣሚ አንሶላም ታሪክም ተጋርተዋል….ስለዚህ ጉዳዩን እንከአንጀቱ ነው ቃል የገባላቸው፡፡ ነገሩን በትኩረት ሊከታተለው..የምርመራውን ቡድን እራሱ ሊመራው…..
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
የፖሊስ ጣቢያውን በራፍ እንደወጡ አንድ ባለ አይጣማ ቀለም ቪታራ መኪና ፊት ለፊት ቆማ ተመለከቱ፡፡ ወዲው አንድ ቄስ ከውስጡ ወጡና ወደ እነሱ ማምራት ጀመሩ..የተለመደውን ሽፍንፍን አለባበስ የለበሱት አባ ሽፍንፍን ነበሩ..አጠገባቸው ሲደርሱ‹‹እቤት የተቃጠለባችሁ እናንተ ናችሁ?››ሲሉ በተረጋጋ እና በተጐተተ ንግግር ጠየቁ አባ ሽፍንፍን…
‹‹አዎ አባቴ..››አሉ አሮጊቷ ፈጠን ብለው
‹‹ስለ እናንተን ጉዳይ አንድ ወዳጄ ከዚህ ደውሎ ነግሮኝ ከሻሸመኔ ነው የመጣውት…አባ ኃይለ ጊርጊስ እባላለው››
ሶስቱም ደነገጡ…. በተለይ ፖሊሱ፡፡ስለ እኚህ ቄስ ዝና ብዙ ብዙ ሰምቷል..ሰምቶም በልቡ አድንቋቸው ነበር ..ሳይታሰብ ዛሬ በአጋጣሚ በአካል ሊያያቸው ስለቻለ ተደሰተ‹‹..ለምን ፊታቸውን ግልጽ አያደርጉትም? ››ሲል በውስጡ የተፈጠረውን ጥያቄ አብሰለሰለ
‹‹ኦ አባቴ እርሶ ኖት እንዴ ?ምን እንርዳዎት?››አለ ፖሊሱ
‹‹በጣም አመሰግናለው ኩማደር ፡፡አሁን ከሻሸመኔ የመጣውት እንዳልኩህ የእዚህን ቤተሰብ መጐዳት ሰምቼ ነው..እነሱን ፍለጋ ወደ ሰፈራቸው ሄጄ ጐረቤቶቻቸውን ስጠይቅ ወደ እዚህ እንዳመሩ ተነገረኝና ወደ እዚህ መጣው ፡፡ ትንሽ ከእነሱ ጋ ለማውራት ፈልጌያለው..ሁኔታዎች ተስተካክለው እቤታቸውን መልሰን ማሰራት እስክንችል ድረስ እኔ ጋ እንዲሆኑ እፈልጋለው….ወደ ሻሸመኔ ልወስዳቸው ነው፡፡ አንተ የምትፈልጋቸው ከሆነ መጥተህ ልታናግራቸው ወይም ደውለህ እንዲመጡ እና እንዲያናግሩህ ማድረግ ትችላለህ..ምን ይመስልሀል?፡፡››
‹‹ኸረ ጥሩ ሀሳብ ነው›› በደስታ ተስማማ
አባ ሽፍንፍን ኩማደሩን ተሰናበቱና ሄለን እና አያቷን ወደ መኪና ውስጥ እንዲገቡ ጋበዞቸው..ሁለቱም ግራ በመጋባ እና በመደነቅ ውስጥ እንዳሉ… ያለምንም መከራከር እግዚያብሄር ከገቡበት መከራ መዞ ሊያወጣቸው ፈልጎ ቄሱን ወደእነሱ እንደላከላቸው በማመን ያለምንም ማቅማማት በእሺታ ያሏቸውን አደረጉ…ጉዞ ወደሻሸመኔ …
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍2
ልጀንማ ‹‹ስጦታ›› አልላትም!!
#ባለወለድ_ስጦታዎች !
ስጦታ እንደመቀበል የሚያስጠላኝ ነገር የለም ! ስጦታ ….ባፍንጫየ ይውጣ !! ስጦታ የጠላሁት በአጎቴ ምክንያት ነው !! ልጅ እያለን …..ቤተሰብ ዘመድ ወዳጅ ወደቤታችን ሲመጣ የሚሰጠን ስጦታ ያጓጓን ነበር …እንደውም በራቀ ትዝታየ ከሰዎቹ መልክ ይልቅ ስጦታ የያዘ እጃቸውን የማስታወስ አባዜ ነበረብኝ ! የዝምድና ማእረግ ሁሉ የምሰጠው በስጦታው መጠን ነበር!
የመጀመሪያ ደረጃ የዝምድና መዓረግ የሚሰጣቸው ዘመዶች ... ጣፋጭ ይዘው የሚመጡ ኬክ በተለይ (ያኔ ኬክ ብርቅ ነበር )….ሁለተኛ ደረጃ ዘመድ ተብለው የተቀመጡት ደግሞ ፍራፍሬ ይዘው ወደቤታችን ጎራ የሚሉት ናቸው ….ሶስተኛ ደረጃ የዝምድና መዓረግ ላይ ያሉት ተረትና ጨዋታ ታጥቀው የሚመጡ ናቸው ሰባት ቀንድ ሶስት አይን ስላለው ጭራቅ ሲያወሩልን ያመሻሉ ‹ቤድ ታይም ስቶሪ› መሆኑ ነው እንኳን ልንተኛ እንዲቹ ነፍሳችን እንደተጨነቀ ቁልጭ ብለን እናድራለን፡)) አራተኛውና ልዩ የዝምድና መዓረግ የሚሰጠው የእናታችን ወንድም አጎታችን ነው (የሱ ልዩ ነው…የአጎቴ ስጦታ የሆነ የፖለቲካ ሲስተም አለው )
ልጅ ነንና ማን መጣ ሳይሆን ምን ይዞ መጣ ዋናው ጥያቂያችን ነበር … ከአያታችን በስተቀር! …ከሩቅ ገጠር የምትመጣው አያታችን (የእናቴ እናት) እሷ ራሷ የፈጣሪ ስጦታ ነው የምትመስለን … ረዥም ቀጠን ያለች ኮስታራ ሴት ናት ….ግን ስንወዳት አይጣል ! አንዳንዱ ሰው እንዲሁ መገኘቱ ስጦታ ይሆንብን የለ …እንደዛ ነበረች አያታችን ! እንደዛም ሁኖ ታዲያ ስጦታ አታምጣ እንጅ የስጦታዎች ሁሉ ቁልፍ ከንፈሯ ላይ ነው….‹‹ምነው ይሄ ልጅ የተማርቤት ቦርሳው አረጀ›› ካለች አባባ ወዲያውኑ ምን የመሰለ ቦርሳ መግዛቱ አይቀሬ ነው ! ለምን እንደሆነ እንጃ ለማንም የማይበገር የማይመስለኝ ቆፍጣናው አባታችን ለእናቴ እናት ይሽቆጠቆጣል ! እኛን ስትጠራ እሱ ‹‹አቤት›› ሁሉ ይላል፡)) እንግዲህ የስጦታ ማዘዣ ደብዳቤው ላይ ሁሉ የቃል ፊርማ የምታሳርፈው አያታችን ስለሆነችም እንደሆን እንጃ ብቻ እንወዳታለን ! ‹‹አያታችሁ ከፈረመችበት ይሰጣችኋል›› ይባላል ሲቀለድ! እናታችን ታዲያ በዚህ ባህሪያችን እኔም ወንድሜም እህቶቸም ላይ ትበሳጫለች …. ሰው ‹‹ምን ይዠ ልምጣ›› እያለ ከዘመድ ተቆራርጨ ልቅር እንዴ?›› ብላ ቱግ ትልብናለች !
አንድ ቀን ግን እናቴ ‹‹የባህሪ ለውጥ አመጣች›› በጣም ነው የተገረምነው ‹‹ ወንድሟ›› ማለት አጎታችን ስጦታ ሊሰጠኝ ሲል ፈገግ አለች …ከምር ፈገግ አለች …. !! እሱ ስጦታውን ሲያወጣ የሆነች የተንኮል ፈገግታ ፊቷ ላይ አንዣበበችና ‹‹ተቀበል አጎትህ አይደል›› አለችኝ... ጭራሽ? !! በኋላ አይደል እንዴ የማዘር ተንኮል የተገለጠልን ሴት መለኛ ናት የሚባለው በእናቴ ነው የገባኝ፡))
አቤት የማዘር ወንድም ስጦታ ሲገርም . . . እንግዲህ ልክ እንደዓለም ዋንጫ በአራት አመት አንድ ጊዜ ነው ስጦታ የሚሰጠው … ስጦታው ታዲያ ዝም ብሎ አይሰጥም ሂደት አለው ….የመጀመሪያ ቀን ቤታችን የመጣ ጊዜ የሰጠኝ ስጦታ ትዝ ይለኛል! እቤታችን አራት ቀን ከርሞ በአምስተኛው ሊሄድ ሲነሳ ‹‹ኧረግ ረስቸው …አቡቹ ና ስቲ ወዲህ …ስጦታ ገዝቸልህ ረስቸው ›› አለና መጀመሪያ እጁ ጋቢውን እየሰረሰረ ካፖርቱ ላይ ደረሰ ካፖርቱን አልፎ ኮቱ ….ከዛ ከሸሚዙ የደረት ኪስ …..ምዝዝ አድርጎ ምን ቢያወጣ ሩ ነው ?….አንዲት ገና ያልተቀረፀች አዲስ እርሳስ!! እኔማ ያን ሁሉ ቁፋሮ ስመለከት አጎቴ ነዳጅ ሊያወጣ ሁሉ መስሎኝ ነበር፡))
‹‹ይሄው ….ይሄ ተላይ ያለው ማጥፊያው ነው (ይፈነዳ ይመስል በጥንቃቄ እየነካ) …በጣም አትፈግፍገው ቶሎ ያልቃል …ደሞ ስተቀርጥ በምላጭ አባትህ ይቅረጥልህ ….ዘመናዊው መቅረጫ አንዴ ጠርቦ ነው የሚጨርሰው ›› ብሎ ረዥም ምክር ጋር ርሳሷን ሰጠኝ …..ከዛማ ሊፋታኝ ነው እንዴ ….እቤታችን በመጣ ቁጥር ሌላ ስጦታ የለም ‹‹ አቡቹ ያ ርሳስ …እንዴት ነው? ….ጥሩ እየተገለገልክበት ነው? …አዎ በጣም አትቅረጠው… እንደነገርኩህ በምላጭ ….ስእል ደሞ ሳልበት… ስእል ትልቅ ሙያ ነው… ለስእል ዋናው ነገር ርሳስ ነው ርሳስ ካለ ስእል አለ …. አንዳንድ ማስታወሻም ካለ ከጡፍህ ስር በስሱ ለማስታወስ ብትጥፍበት ትችላለህ….በቃልህ ከተያዘልህ በኋላ ታጠፈዋለህ ›› አለኝ ….አጎቴ ሲያካብደው የማውቀው ርሳስ የሆነ ሌላ ተዓምር ነገር መሰለኝ!!
ሌላ ቀን አጎቴ ቤታችን ሲመጣ ደሞ ‹‹ አቡቹ ….ያ ርሳስ ለሂሳብ ጥሩ ነው ….አየህ ሂሳብ እንደሌላው ትምርት አደለም ይሳሳታል ….ስትደምር ትሳሳታለህ ሰው ሁኖ መቸም የማይሳሳት የለም …ስታባዛ ትሳሳታለህ ….በተለይ በተለይ ሰው ሁኖ ሲያካፍል የማይሳሳት የለም …ታዲያ ርሳስ ከሆነ ስትሳሳት ስርዝ ድልዝ የለም በማጥፊያዋ ጠፋ ነው ›› በቃ አጎቴ አዛ አደረገኝ! ….ውይ በምን ቀን ነው ይሄን ርሳስ የተቀበልኩት …የእናቴ የተንኮል ሳቅ ቆይቶ ነው የተገለጠልኝ (ቅጣት መሆኑ ነው) ….
በቃ አጎቴ ስጦታ ከሰጠ እድሜ ልኩን ስለሰጣት ነገር ሲያነሳ ሲጥል ….ስጦታው አላቂ ቢሆንኳ የአጎቴ ምክርና ማስጠንቀቂያ አያልቅም !! እንደዛ አይነት ሰው አጋጥሟችሁ አያውቅም ?….የሆነ ነገረ ሰጥቶ እድሜ ልኩን ስለዛች ነገር አጠቃቀም እንዴት ሊሰጣችሁ እንዳሰበ ….ወሬ ሁሉ ሲያወራ ቀን ከጠፋው ስጦታውን ካሌንደር ያደርገዋል ‹‹ያኔ እንትኑን እንደነገ ልሰጥህ እንደዛሬ ›› እያለ !!
እንደዚህ አይነት ባህሪ ያላቸው ፍቅረኞች አሉኮ ....ለምሳሌ ጓደኛሽን ቀጥረሽው ይዘገይብሽና ደውለሽ " የት ደረስክ " ስትይው " ባለፈው ቅቅል የጋበዝኩብሽ ቤት ደርሻለሁ የኔ ማር ፡))" የቅቅል ግብዣው የፊታችን ግንቦት 20 ሶስት አመት ይሆነዋልኮ:) ሴቶችም አሉ ለ23ኛ አመት ልደትህ ዋሌት ሰጥታህ በሰላሳ ሶስተኛ አመትህ የዋሌቱን አስረኛ አመት በዓል በክትፍ እናክብር የምትል:))
እና የአጎቴ ስጦታ የትዝታ ወለዱ ተከፍሎ አያልቅም!! ዘመዶቻችንኮ ከዛ በኋላ ያመጡት ስጦታ መዓት ተቆጥሮ አያልቅም…. አጎቴ ግን በስጦታ ወለዱ ነበር የሚኖረው !! እንደውም ጭራሸ አንድ ቀን አጎቴ ምናለ.... ለበዓል ዘመዱ ሁሉ እቤት ተሰብስቦ ስጦታውም በዛው ልክ ሲጎርፍልን
‹‹ አቡቹ ….የሰው ስጦታ ቀላል ነገር አይደለም …. ነገ ተምረህ ሰው ስትሆን መክፈልህ አይቀርም! ወረቀት ላይ በዛ በሰጠሁህ ባዲሱ ርሳስ አንድ ባንድ የተሰጠህን መዝግብ፡))›› እንግዲህ ባለፈው አመት የሰጠኝን ርሳስ እኮ ነው ‹‹አዲስ›› የሚለው …የሚገርመው ግን ስንክሳር ስላበዛበት ነው መሰል የአጎቴ ርሳስ ከሌሎች ስጦታዎች ሁሉ የበለጠ መስሎ ይሰማኝ ነበር፡)) ለካስ የቴሌቪዝን ጣቢያዎች ወደው አይደለም አንድን ነገር ደጋግመው ደጋግመው ህዝቡን የሚያዝጉት ሲቆይ ህዝቡ የሚወራው ነገር ተራ ቢሆን እንኳን ውድና ትልቅ ነገር ይመስለዋል፡))
ታዲያ ይሄ አጎቴ አንድ ቀን አያቴ ባለችበት ቤተሰቡ ተሰብስቦ እሱም በእንግድነት መጥቶ ….ከኪሱ የፀጉር ማሰሪያ ሻሽ ነገር አወጣና ‹‹ይሄ ላንች ነው ›› አላት እህቴን …ስጦታ ሳይሆን ሽጉጥ የተመዘዘባት ይመስል ልትሮጥ ነበር ቀጠል አደርጎም …‹‹ጠጉር አቧራ ሲጠጣ ከዋለ ፎረፎር ነው የሚፈጥረው …ፀሃይም ቢሆን ቀላል ነገር አይደለም …ይችን ሸብ ካደረግሽ በቃ …አቧራ የለ የሰው አይን የለ ….አንዳንዴ ሰንፈሽ ባታበጥሪው እንኳ መከሌ ይሆንሻል . . . ባይሆን አያትሽ ተፈረመችበት ነው የሚሰጥሽ ›› አለና ወደአያቴ በኩራት ዞረ …(አያቴ ስጦታውን ይሁን ካለች ማለቱ ነው )…ድንገት እኔም
#ባለወለድ_ስጦታዎች !
ስጦታ እንደመቀበል የሚያስጠላኝ ነገር የለም ! ስጦታ ….ባፍንጫየ ይውጣ !! ስጦታ የጠላሁት በአጎቴ ምክንያት ነው !! ልጅ እያለን …..ቤተሰብ ዘመድ ወዳጅ ወደቤታችን ሲመጣ የሚሰጠን ስጦታ ያጓጓን ነበር …እንደውም በራቀ ትዝታየ ከሰዎቹ መልክ ይልቅ ስጦታ የያዘ እጃቸውን የማስታወስ አባዜ ነበረብኝ ! የዝምድና ማእረግ ሁሉ የምሰጠው በስጦታው መጠን ነበር!
የመጀመሪያ ደረጃ የዝምድና መዓረግ የሚሰጣቸው ዘመዶች ... ጣፋጭ ይዘው የሚመጡ ኬክ በተለይ (ያኔ ኬክ ብርቅ ነበር )….ሁለተኛ ደረጃ ዘመድ ተብለው የተቀመጡት ደግሞ ፍራፍሬ ይዘው ወደቤታችን ጎራ የሚሉት ናቸው ….ሶስተኛ ደረጃ የዝምድና መዓረግ ላይ ያሉት ተረትና ጨዋታ ታጥቀው የሚመጡ ናቸው ሰባት ቀንድ ሶስት አይን ስላለው ጭራቅ ሲያወሩልን ያመሻሉ ‹ቤድ ታይም ስቶሪ› መሆኑ ነው እንኳን ልንተኛ እንዲቹ ነፍሳችን እንደተጨነቀ ቁልጭ ብለን እናድራለን፡)) አራተኛውና ልዩ የዝምድና መዓረግ የሚሰጠው የእናታችን ወንድም አጎታችን ነው (የሱ ልዩ ነው…የአጎቴ ስጦታ የሆነ የፖለቲካ ሲስተም አለው )
ልጅ ነንና ማን መጣ ሳይሆን ምን ይዞ መጣ ዋናው ጥያቂያችን ነበር … ከአያታችን በስተቀር! …ከሩቅ ገጠር የምትመጣው አያታችን (የእናቴ እናት) እሷ ራሷ የፈጣሪ ስጦታ ነው የምትመስለን … ረዥም ቀጠን ያለች ኮስታራ ሴት ናት ….ግን ስንወዳት አይጣል ! አንዳንዱ ሰው እንዲሁ መገኘቱ ስጦታ ይሆንብን የለ …እንደዛ ነበረች አያታችን ! እንደዛም ሁኖ ታዲያ ስጦታ አታምጣ እንጅ የስጦታዎች ሁሉ ቁልፍ ከንፈሯ ላይ ነው….‹‹ምነው ይሄ ልጅ የተማርቤት ቦርሳው አረጀ›› ካለች አባባ ወዲያውኑ ምን የመሰለ ቦርሳ መግዛቱ አይቀሬ ነው ! ለምን እንደሆነ እንጃ ለማንም የማይበገር የማይመስለኝ ቆፍጣናው አባታችን ለእናቴ እናት ይሽቆጠቆጣል ! እኛን ስትጠራ እሱ ‹‹አቤት›› ሁሉ ይላል፡)) እንግዲህ የስጦታ ማዘዣ ደብዳቤው ላይ ሁሉ የቃል ፊርማ የምታሳርፈው አያታችን ስለሆነችም እንደሆን እንጃ ብቻ እንወዳታለን ! ‹‹አያታችሁ ከፈረመችበት ይሰጣችኋል›› ይባላል ሲቀለድ! እናታችን ታዲያ በዚህ ባህሪያችን እኔም ወንድሜም እህቶቸም ላይ ትበሳጫለች …. ሰው ‹‹ምን ይዠ ልምጣ›› እያለ ከዘመድ ተቆራርጨ ልቅር እንዴ?›› ብላ ቱግ ትልብናለች !
አንድ ቀን ግን እናቴ ‹‹የባህሪ ለውጥ አመጣች›› በጣም ነው የተገረምነው ‹‹ ወንድሟ›› ማለት አጎታችን ስጦታ ሊሰጠኝ ሲል ፈገግ አለች …ከምር ፈገግ አለች …. !! እሱ ስጦታውን ሲያወጣ የሆነች የተንኮል ፈገግታ ፊቷ ላይ አንዣበበችና ‹‹ተቀበል አጎትህ አይደል›› አለችኝ... ጭራሽ? !! በኋላ አይደል እንዴ የማዘር ተንኮል የተገለጠልን ሴት መለኛ ናት የሚባለው በእናቴ ነው የገባኝ፡))
አቤት የማዘር ወንድም ስጦታ ሲገርም . . . እንግዲህ ልክ እንደዓለም ዋንጫ በአራት አመት አንድ ጊዜ ነው ስጦታ የሚሰጠው … ስጦታው ታዲያ ዝም ብሎ አይሰጥም ሂደት አለው ….የመጀመሪያ ቀን ቤታችን የመጣ ጊዜ የሰጠኝ ስጦታ ትዝ ይለኛል! እቤታችን አራት ቀን ከርሞ በአምስተኛው ሊሄድ ሲነሳ ‹‹ኧረግ ረስቸው …አቡቹ ና ስቲ ወዲህ …ስጦታ ገዝቸልህ ረስቸው ›› አለና መጀመሪያ እጁ ጋቢውን እየሰረሰረ ካፖርቱ ላይ ደረሰ ካፖርቱን አልፎ ኮቱ ….ከዛ ከሸሚዙ የደረት ኪስ …..ምዝዝ አድርጎ ምን ቢያወጣ ሩ ነው ?….አንዲት ገና ያልተቀረፀች አዲስ እርሳስ!! እኔማ ያን ሁሉ ቁፋሮ ስመለከት አጎቴ ነዳጅ ሊያወጣ ሁሉ መስሎኝ ነበር፡))
‹‹ይሄው ….ይሄ ተላይ ያለው ማጥፊያው ነው (ይፈነዳ ይመስል በጥንቃቄ እየነካ) …በጣም አትፈግፍገው ቶሎ ያልቃል …ደሞ ስተቀርጥ በምላጭ አባትህ ይቅረጥልህ ….ዘመናዊው መቅረጫ አንዴ ጠርቦ ነው የሚጨርሰው ›› ብሎ ረዥም ምክር ጋር ርሳሷን ሰጠኝ …..ከዛማ ሊፋታኝ ነው እንዴ ….እቤታችን በመጣ ቁጥር ሌላ ስጦታ የለም ‹‹ አቡቹ ያ ርሳስ …እንዴት ነው? ….ጥሩ እየተገለገልክበት ነው? …አዎ በጣም አትቅረጠው… እንደነገርኩህ በምላጭ ….ስእል ደሞ ሳልበት… ስእል ትልቅ ሙያ ነው… ለስእል ዋናው ነገር ርሳስ ነው ርሳስ ካለ ስእል አለ …. አንዳንድ ማስታወሻም ካለ ከጡፍህ ስር በስሱ ለማስታወስ ብትጥፍበት ትችላለህ….በቃልህ ከተያዘልህ በኋላ ታጠፈዋለህ ›› አለኝ ….አጎቴ ሲያካብደው የማውቀው ርሳስ የሆነ ሌላ ተዓምር ነገር መሰለኝ!!
ሌላ ቀን አጎቴ ቤታችን ሲመጣ ደሞ ‹‹ አቡቹ ….ያ ርሳስ ለሂሳብ ጥሩ ነው ….አየህ ሂሳብ እንደሌላው ትምርት አደለም ይሳሳታል ….ስትደምር ትሳሳታለህ ሰው ሁኖ መቸም የማይሳሳት የለም …ስታባዛ ትሳሳታለህ ….በተለይ በተለይ ሰው ሁኖ ሲያካፍል የማይሳሳት የለም …ታዲያ ርሳስ ከሆነ ስትሳሳት ስርዝ ድልዝ የለም በማጥፊያዋ ጠፋ ነው ›› በቃ አጎቴ አዛ አደረገኝ! ….ውይ በምን ቀን ነው ይሄን ርሳስ የተቀበልኩት …የእናቴ የተንኮል ሳቅ ቆይቶ ነው የተገለጠልኝ (ቅጣት መሆኑ ነው) ….
በቃ አጎቴ ስጦታ ከሰጠ እድሜ ልኩን ስለሰጣት ነገር ሲያነሳ ሲጥል ….ስጦታው አላቂ ቢሆንኳ የአጎቴ ምክርና ማስጠንቀቂያ አያልቅም !! እንደዛ አይነት ሰው አጋጥሟችሁ አያውቅም ?….የሆነ ነገረ ሰጥቶ እድሜ ልኩን ስለዛች ነገር አጠቃቀም እንዴት ሊሰጣችሁ እንዳሰበ ….ወሬ ሁሉ ሲያወራ ቀን ከጠፋው ስጦታውን ካሌንደር ያደርገዋል ‹‹ያኔ እንትኑን እንደነገ ልሰጥህ እንደዛሬ ›› እያለ !!
እንደዚህ አይነት ባህሪ ያላቸው ፍቅረኞች አሉኮ ....ለምሳሌ ጓደኛሽን ቀጥረሽው ይዘገይብሽና ደውለሽ " የት ደረስክ " ስትይው " ባለፈው ቅቅል የጋበዝኩብሽ ቤት ደርሻለሁ የኔ ማር ፡))" የቅቅል ግብዣው የፊታችን ግንቦት 20 ሶስት አመት ይሆነዋልኮ:) ሴቶችም አሉ ለ23ኛ አመት ልደትህ ዋሌት ሰጥታህ በሰላሳ ሶስተኛ አመትህ የዋሌቱን አስረኛ አመት በዓል በክትፍ እናክብር የምትል:))
እና የአጎቴ ስጦታ የትዝታ ወለዱ ተከፍሎ አያልቅም!! ዘመዶቻችንኮ ከዛ በኋላ ያመጡት ስጦታ መዓት ተቆጥሮ አያልቅም…. አጎቴ ግን በስጦታ ወለዱ ነበር የሚኖረው !! እንደውም ጭራሸ አንድ ቀን አጎቴ ምናለ.... ለበዓል ዘመዱ ሁሉ እቤት ተሰብስቦ ስጦታውም በዛው ልክ ሲጎርፍልን
‹‹ አቡቹ ….የሰው ስጦታ ቀላል ነገር አይደለም …. ነገ ተምረህ ሰው ስትሆን መክፈልህ አይቀርም! ወረቀት ላይ በዛ በሰጠሁህ ባዲሱ ርሳስ አንድ ባንድ የተሰጠህን መዝግብ፡))›› እንግዲህ ባለፈው አመት የሰጠኝን ርሳስ እኮ ነው ‹‹አዲስ›› የሚለው …የሚገርመው ግን ስንክሳር ስላበዛበት ነው መሰል የአጎቴ ርሳስ ከሌሎች ስጦታዎች ሁሉ የበለጠ መስሎ ይሰማኝ ነበር፡)) ለካስ የቴሌቪዝን ጣቢያዎች ወደው አይደለም አንድን ነገር ደጋግመው ደጋግመው ህዝቡን የሚያዝጉት ሲቆይ ህዝቡ የሚወራው ነገር ተራ ቢሆን እንኳን ውድና ትልቅ ነገር ይመስለዋል፡))
ታዲያ ይሄ አጎቴ አንድ ቀን አያቴ ባለችበት ቤተሰቡ ተሰብስቦ እሱም በእንግድነት መጥቶ ….ከኪሱ የፀጉር ማሰሪያ ሻሽ ነገር አወጣና ‹‹ይሄ ላንች ነው ›› አላት እህቴን …ስጦታ ሳይሆን ሽጉጥ የተመዘዘባት ይመስል ልትሮጥ ነበር ቀጠል አደርጎም …‹‹ጠጉር አቧራ ሲጠጣ ከዋለ ፎረፎር ነው የሚፈጥረው …ፀሃይም ቢሆን ቀላል ነገር አይደለም …ይችን ሸብ ካደረግሽ በቃ …አቧራ የለ የሰው አይን የለ ….አንዳንዴ ሰንፈሽ ባታበጥሪው እንኳ መከሌ ይሆንሻል . . . ባይሆን አያትሽ ተፈረመችበት ነው የሚሰጥሽ ›› አለና ወደአያቴ በኩራት ዞረ …(አያቴ ስጦታውን ይሁን ካለች ማለቱ ነው )…ድንገት እኔም
👍3❤1
እህቴም ወንድሜም ወደአያቴ ሰፍ ብለን በአንድ ላይ ጮህን ‹‹ እንዳትፈርሚ አያቴ››፡))))))))))
ታዲያ ይሄ አጎቴ በቅርቡ መጣና ‹‹አይ አቡቹ …እስታሁን አላገባህም? ….አልወለድክም ?….ልጅኮ የግዜሄር ስጦታ ነው ›› አለኝ
በሆዴ ‹‹ኧረ እንኳን የአጎት ስጦታ ያልሆነ›› እያልኩ … ዝም አልኩ !
‹‹መቸም ልጅ ስትወልድ እኔ ነኝ ስም የምሰጣት ….አዎ ሴት ተሆነች ስጦታ ብያታለሁ …የአጎትህ ስጦታ ነው በሌላ ስም ትጠራትና ውርድ ከራሴ ›› አለኛ … ህ ?….ልጀንማ ስጦታ ብየ ሳዝነዘንዛት አልኖርም በኛ ይብቃ ትውልድ ይዳን ….
‹‹አቡቹ ››
‹‹አቤት አጎቴ ››
‹‹ ስሙን እንዳትረሳው ….በዛ እርሳስ መዝግብና አስቀምጠው›› ኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡ!!
🔘አሌክስ አብርሃም🔘
ታዲያ ይሄ አጎቴ በቅርቡ መጣና ‹‹አይ አቡቹ …እስታሁን አላገባህም? ….አልወለድክም ?….ልጅኮ የግዜሄር ስጦታ ነው ›› አለኝ
በሆዴ ‹‹ኧረ እንኳን የአጎት ስጦታ ያልሆነ›› እያልኩ … ዝም አልኩ !
‹‹መቸም ልጅ ስትወልድ እኔ ነኝ ስም የምሰጣት ….አዎ ሴት ተሆነች ስጦታ ብያታለሁ …የአጎትህ ስጦታ ነው በሌላ ስም ትጠራትና ውርድ ከራሴ ›› አለኛ … ህ ?….ልጀንማ ስጦታ ብየ ሳዝነዘንዛት አልኖርም በኛ ይብቃ ትውልድ ይዳን ….
‹‹አቡቹ ››
‹‹አቤት አጎቴ ››
‹‹ ስሙን እንዳትረሳው ….በዛ እርሳስ መዝግብና አስቀምጠው›› ኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡ!!
🔘አሌክስ አብርሃም🔘
👍1
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ሀያ
:
✍ድርሰት በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
፨አንቺስ ተነፈሽ እህቴ … ቁስልሽ ትንሽ ጠገገ
የልብሽ ድማት ረግቶ..ፊትሽ በእፎይታ ፈገገ
እኔ ግን በሞት ዝምታ … ውስጤን በበቀል ያነደድኩ
ራሴን ማከም አቅቶኝ …ሙሉ ደስታዬን ያወደምኩ
ባንቺ ቀናሁኝ በሳቅሽ…በታሪክሽም ተደመምኩ
ለራሴ ለሚስኪኑ ግን….እንባዬን በውስጤ አፈሰስኩ
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ሰዓቱ ከምሽቱ ሁለት ሰዓትነው፤ኩማደር መሀሪ ጭላሎ ሆቴል ብቻውን ቁጭ ብሎ ውስኪውን እየተጋተ ነው፡፡እየተጋተ ብዙ ብዙ ነገር ያስባል… አስቦ ይገነባል… የገነባውን መልሶ ያፈርሳል…ማሰቡ ሲሰለቸው.. ከሀሳብ መውጣት እና ዘና ማለት አማረውና አንድ ቆንጆ ሞንዳላ ልጅ ጠራ …እንድታጫውተው፡፡
‹‹አቤት ምን ልታዘዝ?››አለችው አጠገቡ ደርሳ ወደ እሱ ጐንበስ ብላ
‹‹ቁጭ በይ ››አላት..ቁጭ አለች፡፡
ሌላዋ ጓደኛዋ ..ከኃላዋ ተከትላት መጥታ
‹‹ ምን ልታዘዝ ?››ስትል ጠየቀቻት፡፡
‹‹ፋንታ አምጪልኝ›› አዘዘች ፡፡
ልጅቷ ትዕዛዞን ተቀብላ ሄደች፡፡‹‹ምነው ለስላሳ?አልኮል መጠጥ አትደፍሪም ማለት ነው?››ጠየቃት
‹‹ወድጄ ደፍራለው..እዚህ ቦታ እንዲህ አይነት ስራ እየሰራው እንዴት ነው አልኮል ማልደፍረው?እኔ አልኮልን ደፍራላው የአዳም የልጅ ልጆች ደግሞ እኔን ይደፍሩኛል ፡፡…መድፈር..መደፈር..ደስ አይልም ..?››ከትከት ብላ ሳቀች
‹‹አይ እኔ ያልሽው ብዙም አልገባኝም…የጠየኩሽ ፋንታ ስላዘዝሽ ብዬ ነው?››
‹‹ተይዤ ነው..በቃ ያመጡትን ያምጡ ብዬ››
‹‹እነማን ናቸው ያመጡትን የሚያመጡት››
‹‹ባለቤቶቹ ናቸዋ ..››
‹‹አልገባኝም››… የታዘዘችው ልጅ ፋንታ አምጥታ ከፍተችላትና ወደ ቦታዋ ተመለሰች፡፡
ልጅቷም የፍንታ ጠርሙሱን አነሳችና አንዴ ተጐንጭታለት ኩማደሩ ለጠየቃት ጥያቄ መልስ መመለሷን ቀጠለች
‹‹ባለቤቶቹ የእኛን አልኮል መጠጣት እንደ ግዴታ ነው የሚያስቀምጡት››
‹‹ለምን ተብሎ?››
‹‹አየህ አሁን ፋንታ አዘዝኩ..ድገሚ አትለኝም፡፡ ብትለኝም እኔ እሺ ብዬ አልደግምም፡፡ቢራ ቢሆንስ? ቢያንስ ሶስት አራት ጠርሙስ ትጋብዘኛለህ…ካልሆነም እስከ አስር ጠርሙስ ከዛም በላይ ልትጋብዘኝ ትችላለህ.. እንግዲህ ከእኔ መጠጣት ባለቤቶቹ የሚያገኙት ጥቅም ይታይህ….››
‹‹ቆይ ታዲያ ዛሬስ ምነው ..ፍቃድ ተስጥቶሽ ነው?››
‹‹አይደለም.. ጨጎራዬ ተላጠ..ትናንትና አንዱ ጉረኛ ወንድ ሙሉ ውስኪ አውርዶ ለሁለት..እኔ እና እሱ ብቻ ጨረስነው ፡፡ ..እናም ስሰቃይና ሳጐራ ነው ያደርኩት ፤ሀኪም ቤት ሄጄ ኪኒን አዘውልኝ እሱን ውጬ ነው ትንሽ ተንፈስ ያልኩት፡፡ደግሞ ባለቤቶቹ ብቻ አይደሉም እራሱ ጋባዡም ካልጠጣሽ ሞቼ እገኛለው ብሎ እንቡር ይላል..ለእኛ እንኳን የማዘን ፍላጐቱ ባይኖረው እንዴት ለገንዘቡ አያዝንም እያልኩ ሁሌ እገረማለው… ይሄኔ እኮ ለወር የሚሆን የአስቤዛ ወጪ ለሚስቱ አልሰጥም ብሎ እኮ ይሆናል እዚህ መጥቶ እኔን በውስኪ ሲያጠምቀኝ ያደረው…››
‹‹ለመሆኑ ስምሽ ማናው?››
‹‹ከደንበኞቼ ጥያቄዋች ውስጥ በጣም የሚያስጠላኝ ስምሽ ማነው የሚለው ነው?››
‹‹ለምን?››
‹‹እኔም እውነቱን አልነግርህ አንተም ቁምን ነገር ብለህ በአዕምሮህ አትይዘውም..›››
‹‹እንዴት እንዲህ ልትይ ቻልሽ?››
‹‹ከልምድ ነዋ …ከቡና ቤት ሴቶች መካከል 99 ፐርሰንቱ ትክክለኛ ስማቸውን አይናገሩም …ሌላው ደግሞ ስማችሁ ማን ነው ብለው ከሚጠይቁን ደንበኛቻችን መካከለም አብረውንም ቢያድሩ እንኳን 99 ፐርሰንቱ በማግስቱ ቢጠየቁ አያስታውሱትም››
‹‹ትገርሚያለሽ..ለማኛውም ንገሪኝ››
‹‹ከጠቀመህ ትዕግስት እባላለው››
‹‹እውነተኛውን ነው ወይስ የፌኩን ስምሽ ነው የነገርሺኝ፡፡››
‹‹አይ ትክክለኛውን ነው››
‹‹እኔ ደግሞ ኩማደር መሀሪ እባላለው››
‹‹ኩማደር መሀሪ!!!››የአሸባሪ ስም ፊቷ እንደተጠራባት በረገገች፡፡
‹‹ምነው በረገግሽ?››
‹‹በጣም ነው የማውቅህ››
‹‹ማ እኔን? የት? ››
‹‹እዚሁ ነዋ ፡፡ብዙ ሰዎች ስለአንተ ሲያወሩ ሰማለው››
‹‹ምን ምን እያሉ?››
‹‹ያው ..ብቻ ብዙ ብዙ ነገር ያወራሉ….ግን አትመስልም…››
‹‹እንዴት አትመስልም ስትይ?››ንግግሯ ግራ አጋብቶት
‹‹እንዴ ስለአንተ ሲያወሩ እኮ ስለሆነ ግዙፍ አውሬ የሚያወሩ ነው የሚመስለው..ግን እንደዛ አትመስልም፡፡ ብዙም አታስፈራም ..ትጫወታለህ››
‹‹ለማኛውም ከዛሬ ጀምሮ ያው ጓደኛ ሆነናል አይደል?››አላት
‹‹ይመቸኛል››
‹‹አሁን ልሄድ ነው፡፡››
‹‹እንኳንም አብረን እንደር አላልከኝ››አለችው…ፈገግ እያለች፡፡
‹‹ለካ እንደዛም ይባላል.?.ብልሽ ግን ምነው ፈርተሺኝ ነው? ››
‹‹አይ በፍፅም አልፈራውህም፡፡እኔ እንደውም እድሌ ሆኖ ጨካኝ የሚባሉ ሰዎች እጣ ክፍሌ ናቸው፡፡ብቻ እንደነገርኩህ በትናንትናው አዳሬ ድክምክም ስላልኩ ነው፡፡››
‹እንደዛ ከሆነ ተስማምተናል፡፡››ብሎ ሂሳቡን ከፈለና ለእሷም በእጆ ድፍን መቶ ብር እስጨብጧት ሆቴሉን ለቆ ወጣ፡፡
ሰዓቱን ሲመለከት ሶስት ሰዓት ተኩል ሆኖል፡፡ወደቤቱ ሳይሆን ወደፖሊስ ጣቢያ ነበር ያመረው፡፡እስኪሰለቸው ቢሮው ሲሰራ ቆይቶ ስምንት ሰዓት ሲሆን አረፍ ሊል ወደ ቤቱ አመራ…መኪና ስላልያዘ በእግሩ ነው እየተጓዘ የነበረው..ውስጥ ለውስጥ ያለውን ሶስተኛ መንገድ ይዞ ቀበሌ 4 ወደሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ሊደርስ 400 ሜትር ያህል ርቀት ሲቀረው..የሆነ እንቅስቃሴ ከተቃራኒው መንገድ ተመለከተ…ጐኑ የሻጠውን ሽጉጥ መዥረጥ በማድረግ በእጁ ይዞ መንገዱን በፍጥነት ለቆ ወደአጥር በመጠጋት ጨለማ ውስጥ ተከለለ፡፡አዎ አሁን በግልጽ ይታዩታል… ሁለት ጎረምሶች ናቸው፡፡ፈጠን እያሉ ግራና ቀኛቸውን እየተገለማመጡ ነው የሚጓዙት ..አንደኛው በእጁ ጥቁር ሳምሶናይት ሻንጣ ይዞል፡፡የጉዞቸው አቅጣጫ ወደ እሱ ነው፡፡እየቀረቡት ነው….እነሱ ባያዩትም እሱ በግልጽ እያያቸው ነው፡፡አምስት እርምጃ ርቀት ላይ ሲደርሱ
‹‹ባላችሁበት ቁሙ››ቆፍጠን ያለ ትዕዛዝ አሳተላለፈ፡፡ያላሰቡት ዱብዳ የገጠማቸው ሁለት ጓረምሶች ባሉበት ተገትረው ቆመው ፊታቸውን ድምጹን ወደሰሙበት አቅጣጫ መለሱት፡፡
ኩማደሩ ከተወሸቀበት ጭለማ ቀስ እያለ እየተሳበ ወጣ‹‹እጅ ወደ ላይ››
ሳምሳናይቱን መሬት ላይ አስቀምጠው ሁለቱም እጃቸውን በፍራቻ ወደላይ ሰቀሉት
‹‹እሺ በዚህ ሰዓት ከየት ወደ የት ነው?››
‹‹ጓደኞቻችን ቤት ስንቅም ቆይተን… መሽቶብን አሁን ወደ ቤታችን እየገባ ነው››መለሰ አንደኛው
‹‹እሺ …ሳምሳናይቱ ውስጥ ምንድነው ያለው?››
‹‹ምንም አይደል የስራ ዶክመንት ነው››ዋሹት
ድንገት ለሚጠይቀው ጥያቄ መልስ የሚሰጥውን ልጅ ማንነት ለየው፡፡ቢያንስ እሱ ሻሸመኔ ከገባ ጀምሮ ከሶስት ጊዜ በላይ ከስርቆት ወንጀል ጋር በተያያዘ ፖሊስ ጣቢያ አግኝቶታል፡፡
‹‹አጅሬ አወቅኩህ.. አንተው ነህ..አሁን ወደፖሊስ ጣቢያ እንሂድ ወይስ እንደራደር?››
ንግግሩ ስላልገባቸው ፈጥነው ሊመልሱለት አልቻሉም
‹‹በውድቅት ለሊት ብርድ አታስቀጥቅጡን ..ወደፖሊስ ጣቢያ ልውሰዳችሁ ወይስ እንደራደር? መልሳችሁን እየጠበቅኩ ነው?››
››እንደራደር አለ.. እስከአሁን በፀጥታ ውስጥ የነበረው ፈርጣማ ጥቁር ወጣት››
‹‹እንደዛ ከሆነ ሳምሶናይቱን አንሳና ያዘው››አንስቶ ያዘው
‹‹ፊታችሁን ዞራችሁ ቀጥሉ…››
‹‹ወዴት? ›› ጠየቀ አንደኛው
‹‹ድርድራችን ትንሽ ረዘም ያለ እና ጊዜ የሚፈጅ ነው..እዚህ ብርድ ላይ በዚህ ውድቅት ለሊት መደራር ስለማንችል ወደ እኔ ቤት እንሂድ.. አይዞችሁ ደርሰናል ቅርብ ነው››ሽጉጥ ከኃላ እንደደቀነባቸው ነበር…እሱ ቤት ደረሱ… የግቢውን አጥር በር ከፍቶ
:
#ክፍል_ሀያ
:
✍ድርሰት በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
፨አንቺስ ተነፈሽ እህቴ … ቁስልሽ ትንሽ ጠገገ
የልብሽ ድማት ረግቶ..ፊትሽ በእፎይታ ፈገገ
እኔ ግን በሞት ዝምታ … ውስጤን በበቀል ያነደድኩ
ራሴን ማከም አቅቶኝ …ሙሉ ደስታዬን ያወደምኩ
ባንቺ ቀናሁኝ በሳቅሽ…በታሪክሽም ተደመምኩ
ለራሴ ለሚስኪኑ ግን….እንባዬን በውስጤ አፈሰስኩ
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ሰዓቱ ከምሽቱ ሁለት ሰዓትነው፤ኩማደር መሀሪ ጭላሎ ሆቴል ብቻውን ቁጭ ብሎ ውስኪውን እየተጋተ ነው፡፡እየተጋተ ብዙ ብዙ ነገር ያስባል… አስቦ ይገነባል… የገነባውን መልሶ ያፈርሳል…ማሰቡ ሲሰለቸው.. ከሀሳብ መውጣት እና ዘና ማለት አማረውና አንድ ቆንጆ ሞንዳላ ልጅ ጠራ …እንድታጫውተው፡፡
‹‹አቤት ምን ልታዘዝ?››አለችው አጠገቡ ደርሳ ወደ እሱ ጐንበስ ብላ
‹‹ቁጭ በይ ››አላት..ቁጭ አለች፡፡
ሌላዋ ጓደኛዋ ..ከኃላዋ ተከትላት መጥታ
‹‹ ምን ልታዘዝ ?››ስትል ጠየቀቻት፡፡
‹‹ፋንታ አምጪልኝ›› አዘዘች ፡፡
ልጅቷ ትዕዛዞን ተቀብላ ሄደች፡፡‹‹ምነው ለስላሳ?አልኮል መጠጥ አትደፍሪም ማለት ነው?››ጠየቃት
‹‹ወድጄ ደፍራለው..እዚህ ቦታ እንዲህ አይነት ስራ እየሰራው እንዴት ነው አልኮል ማልደፍረው?እኔ አልኮልን ደፍራላው የአዳም የልጅ ልጆች ደግሞ እኔን ይደፍሩኛል ፡፡…መድፈር..መደፈር..ደስ አይልም ..?››ከትከት ብላ ሳቀች
‹‹አይ እኔ ያልሽው ብዙም አልገባኝም…የጠየኩሽ ፋንታ ስላዘዝሽ ብዬ ነው?››
‹‹ተይዤ ነው..በቃ ያመጡትን ያምጡ ብዬ››
‹‹እነማን ናቸው ያመጡትን የሚያመጡት››
‹‹ባለቤቶቹ ናቸዋ ..››
‹‹አልገባኝም››… የታዘዘችው ልጅ ፋንታ አምጥታ ከፍተችላትና ወደ ቦታዋ ተመለሰች፡፡
ልጅቷም የፍንታ ጠርሙሱን አነሳችና አንዴ ተጐንጭታለት ኩማደሩ ለጠየቃት ጥያቄ መልስ መመለሷን ቀጠለች
‹‹ባለቤቶቹ የእኛን አልኮል መጠጣት እንደ ግዴታ ነው የሚያስቀምጡት››
‹‹ለምን ተብሎ?››
‹‹አየህ አሁን ፋንታ አዘዝኩ..ድገሚ አትለኝም፡፡ ብትለኝም እኔ እሺ ብዬ አልደግምም፡፡ቢራ ቢሆንስ? ቢያንስ ሶስት አራት ጠርሙስ ትጋብዘኛለህ…ካልሆነም እስከ አስር ጠርሙስ ከዛም በላይ ልትጋብዘኝ ትችላለህ.. እንግዲህ ከእኔ መጠጣት ባለቤቶቹ የሚያገኙት ጥቅም ይታይህ….››
‹‹ቆይ ታዲያ ዛሬስ ምነው ..ፍቃድ ተስጥቶሽ ነው?››
‹‹አይደለም.. ጨጎራዬ ተላጠ..ትናንትና አንዱ ጉረኛ ወንድ ሙሉ ውስኪ አውርዶ ለሁለት..እኔ እና እሱ ብቻ ጨረስነው ፡፡ ..እናም ስሰቃይና ሳጐራ ነው ያደርኩት ፤ሀኪም ቤት ሄጄ ኪኒን አዘውልኝ እሱን ውጬ ነው ትንሽ ተንፈስ ያልኩት፡፡ደግሞ ባለቤቶቹ ብቻ አይደሉም እራሱ ጋባዡም ካልጠጣሽ ሞቼ እገኛለው ብሎ እንቡር ይላል..ለእኛ እንኳን የማዘን ፍላጐቱ ባይኖረው እንዴት ለገንዘቡ አያዝንም እያልኩ ሁሌ እገረማለው… ይሄኔ እኮ ለወር የሚሆን የአስቤዛ ወጪ ለሚስቱ አልሰጥም ብሎ እኮ ይሆናል እዚህ መጥቶ እኔን በውስኪ ሲያጠምቀኝ ያደረው…››
‹‹ለመሆኑ ስምሽ ማናው?››
‹‹ከደንበኞቼ ጥያቄዋች ውስጥ በጣም የሚያስጠላኝ ስምሽ ማነው የሚለው ነው?››
‹‹ለምን?››
‹‹እኔም እውነቱን አልነግርህ አንተም ቁምን ነገር ብለህ በአዕምሮህ አትይዘውም..›››
‹‹እንዴት እንዲህ ልትይ ቻልሽ?››
‹‹ከልምድ ነዋ …ከቡና ቤት ሴቶች መካከል 99 ፐርሰንቱ ትክክለኛ ስማቸውን አይናገሩም …ሌላው ደግሞ ስማችሁ ማን ነው ብለው ከሚጠይቁን ደንበኛቻችን መካከለም አብረውንም ቢያድሩ እንኳን 99 ፐርሰንቱ በማግስቱ ቢጠየቁ አያስታውሱትም››
‹‹ትገርሚያለሽ..ለማኛውም ንገሪኝ››
‹‹ከጠቀመህ ትዕግስት እባላለው››
‹‹እውነተኛውን ነው ወይስ የፌኩን ስምሽ ነው የነገርሺኝ፡፡››
‹‹አይ ትክክለኛውን ነው››
‹‹እኔ ደግሞ ኩማደር መሀሪ እባላለው››
‹‹ኩማደር መሀሪ!!!››የአሸባሪ ስም ፊቷ እንደተጠራባት በረገገች፡፡
‹‹ምነው በረገግሽ?››
‹‹በጣም ነው የማውቅህ››
‹‹ማ እኔን? የት? ››
‹‹እዚሁ ነዋ ፡፡ብዙ ሰዎች ስለአንተ ሲያወሩ ሰማለው››
‹‹ምን ምን እያሉ?››
‹‹ያው ..ብቻ ብዙ ብዙ ነገር ያወራሉ….ግን አትመስልም…››
‹‹እንዴት አትመስልም ስትይ?››ንግግሯ ግራ አጋብቶት
‹‹እንዴ ስለአንተ ሲያወሩ እኮ ስለሆነ ግዙፍ አውሬ የሚያወሩ ነው የሚመስለው..ግን እንደዛ አትመስልም፡፡ ብዙም አታስፈራም ..ትጫወታለህ››
‹‹ለማኛውም ከዛሬ ጀምሮ ያው ጓደኛ ሆነናል አይደል?››አላት
‹‹ይመቸኛል››
‹‹አሁን ልሄድ ነው፡፡››
‹‹እንኳንም አብረን እንደር አላልከኝ››አለችው…ፈገግ እያለች፡፡
‹‹ለካ እንደዛም ይባላል.?.ብልሽ ግን ምነው ፈርተሺኝ ነው? ››
‹‹አይ በፍፅም አልፈራውህም፡፡እኔ እንደውም እድሌ ሆኖ ጨካኝ የሚባሉ ሰዎች እጣ ክፍሌ ናቸው፡፡ብቻ እንደነገርኩህ በትናንትናው አዳሬ ድክምክም ስላልኩ ነው፡፡››
‹እንደዛ ከሆነ ተስማምተናል፡፡››ብሎ ሂሳቡን ከፈለና ለእሷም በእጆ ድፍን መቶ ብር እስጨብጧት ሆቴሉን ለቆ ወጣ፡፡
ሰዓቱን ሲመለከት ሶስት ሰዓት ተኩል ሆኖል፡፡ወደቤቱ ሳይሆን ወደፖሊስ ጣቢያ ነበር ያመረው፡፡እስኪሰለቸው ቢሮው ሲሰራ ቆይቶ ስምንት ሰዓት ሲሆን አረፍ ሊል ወደ ቤቱ አመራ…መኪና ስላልያዘ በእግሩ ነው እየተጓዘ የነበረው..ውስጥ ለውስጥ ያለውን ሶስተኛ መንገድ ይዞ ቀበሌ 4 ወደሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ሊደርስ 400 ሜትር ያህል ርቀት ሲቀረው..የሆነ እንቅስቃሴ ከተቃራኒው መንገድ ተመለከተ…ጐኑ የሻጠውን ሽጉጥ መዥረጥ በማድረግ በእጁ ይዞ መንገዱን በፍጥነት ለቆ ወደአጥር በመጠጋት ጨለማ ውስጥ ተከለለ፡፡አዎ አሁን በግልጽ ይታዩታል… ሁለት ጎረምሶች ናቸው፡፡ፈጠን እያሉ ግራና ቀኛቸውን እየተገለማመጡ ነው የሚጓዙት ..አንደኛው በእጁ ጥቁር ሳምሶናይት ሻንጣ ይዞል፡፡የጉዞቸው አቅጣጫ ወደ እሱ ነው፡፡እየቀረቡት ነው….እነሱ ባያዩትም እሱ በግልጽ እያያቸው ነው፡፡አምስት እርምጃ ርቀት ላይ ሲደርሱ
‹‹ባላችሁበት ቁሙ››ቆፍጠን ያለ ትዕዛዝ አሳተላለፈ፡፡ያላሰቡት ዱብዳ የገጠማቸው ሁለት ጓረምሶች ባሉበት ተገትረው ቆመው ፊታቸውን ድምጹን ወደሰሙበት አቅጣጫ መለሱት፡፡
ኩማደሩ ከተወሸቀበት ጭለማ ቀስ እያለ እየተሳበ ወጣ‹‹እጅ ወደ ላይ››
ሳምሳናይቱን መሬት ላይ አስቀምጠው ሁለቱም እጃቸውን በፍራቻ ወደላይ ሰቀሉት
‹‹እሺ በዚህ ሰዓት ከየት ወደ የት ነው?››
‹‹ጓደኞቻችን ቤት ስንቅም ቆይተን… መሽቶብን አሁን ወደ ቤታችን እየገባ ነው››መለሰ አንደኛው
‹‹እሺ …ሳምሳናይቱ ውስጥ ምንድነው ያለው?››
‹‹ምንም አይደል የስራ ዶክመንት ነው››ዋሹት
ድንገት ለሚጠይቀው ጥያቄ መልስ የሚሰጥውን ልጅ ማንነት ለየው፡፡ቢያንስ እሱ ሻሸመኔ ከገባ ጀምሮ ከሶስት ጊዜ በላይ ከስርቆት ወንጀል ጋር በተያያዘ ፖሊስ ጣቢያ አግኝቶታል፡፡
‹‹አጅሬ አወቅኩህ.. አንተው ነህ..አሁን ወደፖሊስ ጣቢያ እንሂድ ወይስ እንደራደር?››
ንግግሩ ስላልገባቸው ፈጥነው ሊመልሱለት አልቻሉም
‹‹በውድቅት ለሊት ብርድ አታስቀጥቅጡን ..ወደፖሊስ ጣቢያ ልውሰዳችሁ ወይስ እንደራደር? መልሳችሁን እየጠበቅኩ ነው?››
››እንደራደር አለ.. እስከአሁን በፀጥታ ውስጥ የነበረው ፈርጣማ ጥቁር ወጣት››
‹‹እንደዛ ከሆነ ሳምሶናይቱን አንሳና ያዘው››አንስቶ ያዘው
‹‹ፊታችሁን ዞራችሁ ቀጥሉ…››
‹‹ወዴት? ›› ጠየቀ አንደኛው
‹‹ድርድራችን ትንሽ ረዘም ያለ እና ጊዜ የሚፈጅ ነው..እዚህ ብርድ ላይ በዚህ ውድቅት ለሊት መደራር ስለማንችል ወደ እኔ ቤት እንሂድ.. አይዞችሁ ደርሰናል ቅርብ ነው››ሽጉጥ ከኃላ እንደደቀነባቸው ነበር…እሱ ቤት ደረሱ… የግቢውን አጥር በር ከፍቶ
👍4❤1
አስገባቸው..መልሶ ቆለፋው …ሽጉጥ የያዘውን እጁን እነሱ ላይ እንደደቀነ በአንድ እጁ የቤቱን በራፍ ከፈተና..‹‹የተከበራችሁ እንግዶቼ ግቡ ››በማለት ጋበዛቸው.. እነሱም ግራ እንደተጋቡ በዝግታ ወደውስጥ ገቡ ፡፡መልሶ ቀረቀረውና ቁልፉን ኪሱን ውስጥ ከተተው፡፡
‹‹ተቀመጡ …ዘና በሉ ››ሶፋውን ጥለው ደረቅ ወንበሩ ላይ ጐን ለጐን ተቀመጡ
ልብስ ቀይሬ ልምጣ በማለት እስከአሁን ደቅኖባቸው የነበረውን ሽጉጥ እዛው እነሱ ፊት ለፈት የሚገኝ ጠረጵዛ ላይ ወርወር አድርጎት ወደመኝታ ቤት ገባ፡፡
ግራ ተጋቡ..አላመኑም..እርስ በርስ ተያዩ፡፡‹‹ባሪች አንሳው…››አለው ኤልያስ የተባለው ወጣት
‹‹ምኑን ››መልሶ ጠየቀው አንሳው ያለው ምኑን እንደሆነ እያወቀ ግን ስለፈራ
‹‹ሽጉጡን ነዋ…አስፈራርተን እንዲለቀን እናደርጋለን፡፡›› አለው በሹክሹክታ
‹‹ምን ነካህ አምልጠንስ? አሳዶ ይይዘናል..ማን መሰለህ ?ኩማደሩ እኮ ነው፡፡››መለሰ ባርያው የሚባለው፡፡
‹‹እሺ እንግደለዋ..እኛ እንደሆን ማን ይጠረጥራል..በራሱ ሽጉጥ ደፍተነው እንሂድ››የተሸለ ያለውን ሀሳብ አቀረበ
‹‹እኔ አንጃ ቢቀርብን እና የሚለንን ብንሰማ ይሻል ይመስለኛል››አሁንም ሁኔታውን ስላላማረውና ውስጡም በጣም ስለፈራ ተቃወመ….
ኤልያስ ግን ተሳበና ከጠረጵዛው ላይ ሽጉጡን አነሳ ..ልክ አንስቶ ወደፊት ሲቀስር ኩማደሩ ቢጃማውን ለብሶ የወስኪ ጠርሙስ ከሶስት ብርጭቆ ጋር ይዞ ከመኝታ ክፍሉ ሲወጣ ተገጣጠሙ ፡፡
‹‹አስጠበቅኮችሁ አይደል …››
‹‹ባክህ ባለህት ቁም›› አንባረቀበት ኤልያስ
‹‹ኸረ ተረጋጋ… ሰው ሰው ቤት በእንግድነት መጥቶ ባለቤቱን እንዴት እንዲህ ያመናጭቃል.. ?አረ ነውር ነው››አለው ኩማንዳሩ ተረጋቶ
ኤልያስ ተበሳጨ‹‹እየቀለድኩ አይደለውም… አሁን ቁልፉን አውጣና በራፉን ክፈትልን በሰላም እንሂድበት ..ካለበለዛ ግንባርህን ነው ምፈረክሰው››አለ ሽጉጡን እንደደቀነበት ከመቀመጫው ተነስቶ ..ባሪያውም ተከትሎት ተነስቶ ከጐኑ በመቆም ግራ በመጋባት አይኑን ማቁለጭለጭ ጀመረ፡፡
‹‹አይ ውይይታችንን አከናውነን ከተስማማን ወደቤታችሁ ካልተስማማን ደግሞ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ነው የምትሄዱት እንጂ እንደዚህማ አይሆንም ››አላቸው
‹‹ሰውዬ አይታይህም እንዴ ?የገዛ ሽጉጥህን ደቅኜብሀለው እኮ!!!››
‹‹እንግዲያው የሚከፈትላችሁ በር የለም …በምልህ ካልተስማማህ ተኩስ››አለው በልበሙሉነት
‹‹ካልክ እንግዲህ….›› ብሎ ኢላማውን አስተካከለ…፡፡ባሪያው ተጨንቆ ‹‹ተው ኤልያስ ይቅርብን ››ሲል ለማስጠንቀቅ ሞከረ …ግልፍተኛው እና ችኩሉ ኤልያስ ግን ሊሰማው አልፈቀደም…የሽጉጡን አፈ ሙዝ በኩማደር መሀሪ ግንባር አስተካክሎ ቃታውን ሳበ…..
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
‹‹ተቀመጡ …ዘና በሉ ››ሶፋውን ጥለው ደረቅ ወንበሩ ላይ ጐን ለጐን ተቀመጡ
ልብስ ቀይሬ ልምጣ በማለት እስከአሁን ደቅኖባቸው የነበረውን ሽጉጥ እዛው እነሱ ፊት ለፈት የሚገኝ ጠረጵዛ ላይ ወርወር አድርጎት ወደመኝታ ቤት ገባ፡፡
ግራ ተጋቡ..አላመኑም..እርስ በርስ ተያዩ፡፡‹‹ባሪች አንሳው…››አለው ኤልያስ የተባለው ወጣት
‹‹ምኑን ››መልሶ ጠየቀው አንሳው ያለው ምኑን እንደሆነ እያወቀ ግን ስለፈራ
‹‹ሽጉጡን ነዋ…አስፈራርተን እንዲለቀን እናደርጋለን፡፡›› አለው በሹክሹክታ
‹‹ምን ነካህ አምልጠንስ? አሳዶ ይይዘናል..ማን መሰለህ ?ኩማደሩ እኮ ነው፡፡››መለሰ ባርያው የሚባለው፡፡
‹‹እሺ እንግደለዋ..እኛ እንደሆን ማን ይጠረጥራል..በራሱ ሽጉጥ ደፍተነው እንሂድ››የተሸለ ያለውን ሀሳብ አቀረበ
‹‹እኔ አንጃ ቢቀርብን እና የሚለንን ብንሰማ ይሻል ይመስለኛል››አሁንም ሁኔታውን ስላላማረውና ውስጡም በጣም ስለፈራ ተቃወመ….
ኤልያስ ግን ተሳበና ከጠረጵዛው ላይ ሽጉጡን አነሳ ..ልክ አንስቶ ወደፊት ሲቀስር ኩማደሩ ቢጃማውን ለብሶ የወስኪ ጠርሙስ ከሶስት ብርጭቆ ጋር ይዞ ከመኝታ ክፍሉ ሲወጣ ተገጣጠሙ ፡፡
‹‹አስጠበቅኮችሁ አይደል …››
‹‹ባክህ ባለህት ቁም›› አንባረቀበት ኤልያስ
‹‹ኸረ ተረጋጋ… ሰው ሰው ቤት በእንግድነት መጥቶ ባለቤቱን እንዴት እንዲህ ያመናጭቃል.. ?አረ ነውር ነው››አለው ኩማንዳሩ ተረጋቶ
ኤልያስ ተበሳጨ‹‹እየቀለድኩ አይደለውም… አሁን ቁልፉን አውጣና በራፉን ክፈትልን በሰላም እንሂድበት ..ካለበለዛ ግንባርህን ነው ምፈረክሰው››አለ ሽጉጡን እንደደቀነበት ከመቀመጫው ተነስቶ ..ባሪያውም ተከትሎት ተነስቶ ከጐኑ በመቆም ግራ በመጋባት አይኑን ማቁለጭለጭ ጀመረ፡፡
‹‹አይ ውይይታችንን አከናውነን ከተስማማን ወደቤታችሁ ካልተስማማን ደግሞ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ነው የምትሄዱት እንጂ እንደዚህማ አይሆንም ››አላቸው
‹‹ሰውዬ አይታይህም እንዴ ?የገዛ ሽጉጥህን ደቅኜብሀለው እኮ!!!››
‹‹እንግዲያው የሚከፈትላችሁ በር የለም …በምልህ ካልተስማማህ ተኩስ››አለው በልበሙሉነት
‹‹ካልክ እንግዲህ….›› ብሎ ኢላማውን አስተካከለ…፡፡ባሪያው ተጨንቆ ‹‹ተው ኤልያስ ይቅርብን ››ሲል ለማስጠንቀቅ ሞከረ …ግልፍተኛው እና ችኩሉ ኤልያስ ግን ሊሰማው አልፈቀደም…የሽጉጡን አፈ ሙዝ በኩማደር መሀሪ ግንባር አስተካክሎ ቃታውን ሳበ…..
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍2❤1
#እንዴት_ነህ_አቦወለድ
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ከቶ እንደምን አለህ
ኑሮ እንዴት ይዞሃል
አሁንም ልጅ ነህ ወይ
ወይስ ጎርምስሃል
መጎርመሱንማ ጎርምሰን ነበረ
የቀመስነው ሁሉ ኮምጣጤ ሆኖብን ከሬት የመረረ
እንዳንተ ሚጣፍጥ የልጅነት ጊዜ ናፍቆን እንደቀረ
ቀልድ ሁሉ ጠፍቶብን የፊታችን ጅማት በመናደድ ብዛት እንደተገተረ
መጎርመሱንማ ጎርምሰን ነበረ
....እንዴት ነህ አቦ'ለድ .......!
የልደታችን ቀን
ከሻማችን ጀርባ
ከእስታር ብጥብጥ ጣገብ ከፈንዲሻው በላይ የምትቀመጠው
ሁለት ብር ለሌለን
እሽግህን ፈጠህ በችርቻሮ ዋጋ በስሙኒ ሂሳብ ሱቅ የምትሸጠው
ጠጠር ከረሜላን
ጋሌጣ ብስኩትን
የፉትቦል ማስቲካን በዋጋ ምትበልጠው
እንዴት ነህ አቡወለድ እንዴት ነህ ሳቂታው
የኛን አትጠይቀኝ የኛ እዳ ገብስ ነው
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
አቡወለድ
በኢቶጲስ ዘመን ልጆች የማይታወቅ የማይወደድ
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ከቶ እንደምን አለህ
ኑሮ እንዴት ይዞሃል
አሁንም ልጅ ነህ ወይ
ወይስ ጎርምስሃል
መጎርመሱንማ ጎርምሰን ነበረ
የቀመስነው ሁሉ ኮምጣጤ ሆኖብን ከሬት የመረረ
እንዳንተ ሚጣፍጥ የልጅነት ጊዜ ናፍቆን እንደቀረ
ቀልድ ሁሉ ጠፍቶብን የፊታችን ጅማት በመናደድ ብዛት እንደተገተረ
መጎርመሱንማ ጎርምሰን ነበረ
....እንዴት ነህ አቦ'ለድ .......!
የልደታችን ቀን
ከሻማችን ጀርባ
ከእስታር ብጥብጥ ጣገብ ከፈንዲሻው በላይ የምትቀመጠው
ሁለት ብር ለሌለን
እሽግህን ፈጠህ በችርቻሮ ዋጋ በስሙኒ ሂሳብ ሱቅ የምትሸጠው
ጠጠር ከረሜላን
ጋሌጣ ብስኩትን
የፉትቦል ማስቲካን በዋጋ ምትበልጠው
እንዴት ነህ አቡወለድ እንዴት ነህ ሳቂታው
የኛን አትጠይቀኝ የኛ እዳ ገብስ ነው
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
አቡወለድ
በኢቶጲስ ዘመን ልጆች የማይታወቅ የማይወደድ
👍2
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ሀያ_አንድ
:
✍ድርሰት:-በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
..ኤልያስ ምላጩን ሳበው …ቀጭ የሚል ድምጽ እንጂ ዷ የሚል ፍንዳታ ወይም ጨኸት አልተሰማም ፡፡ ግራ በመጋት እራሱ ደነገጠ..ተስፋ ባለመቁረጥ ዳግመኛ ሞከረ … መልሶ ምላጩን ሳበው..አሁንም ቀጭ የሚል ተመሳሳይ ድምፅ ነው የተሰማው፡፡
በዚህ ጊዜ ግን ለኤልያስ እንቅስቃሴ ብዙም ትኩረት ሳይሰጥ ኮማንደሩ የያዘውን የውስኪ ጠርሙስ እና ብርጭቆ ጠረጵዛው ላይ አስቀመጠና ከለበሰው የቢጃማ ኪስ ውስጥ አንድ በመጠኗ በጣም አነስተኛ የሆነች ሽጉጥ አወጣና ወደ እነሱ አቅጣጫ አነጣጠረ እና ተኮሰ፡፡ ቷ..የሚል እስደንጋጭ ድምጽ አሰማች ..ሽጉጧ፡፡ ሁለቱም ግራና ቀኝ ፍንችር ብለው ወደቁ ..ሌላ ተመልካች ሰው ቢኖር ኖሮ እንዴት አድርጐ ቢተኩስ እንዴት አድርጎ ቢያነጣጥር ነው በአንድ ተኩስ እና በአንድ ጥይት ሁለቱን ያነጠፋቸው ብሎ ይገረም ነበር፡፡ኩማደሩ ግን ሽጉጡን በግራ እጁ እንደያዘ በቀኝ እጁ የውስኪውን ጠርሙስ አንስቶ በሶስቱም ብርጭቆ ላይ ቀድቶ እስኪያጠናቅቅ ሁለቱም በድንጋጤ በተጋደሙበት እንዳሉ ነበሩ፡፡
‹‹ኸረ ተነሱ ግድግዳው ለተመታው እናንተ ምን አዘረራችሁ?››
በሰመመን ሰሙትና እንደምንም ተነስተው እየተዞዞሩ እራሳቸውን በእርግጥ አለመመታቸውን ለማረጋገጥ ፈተሹ …በአንድነት ወደኃላቸው ዞረው ከጀርባቸው ያለውን ግድግዳ ተመለከቱ …ጥይቷ ግድግዳውን በስታዋለች፡፡
‹‹ቁጭ በሉ..ግን ላስጠንቅሰቃችሁ ከአሁን ቡኃላ ብታበሳጩኝ ግድግዳውን ሳይሆን ግንባራችሁን ነው የምፈረክሰው፡፡›› ፈራ ተባ እያሉ ወደመቀመጫቸው ተመለሱ፡፡ ውስኪ የተቀዳበትን ብርጭቆ አቀበላቸው እና የራሱን ይዞ ተቀመጠ፡፡
‹‹እኔ ካላወቃችሁኝ ኩማንደር መሀሪ እባላለው..የእናንተስ?››
‹‹እኔ ባርያው እባላለው ››አለው ጠቆር ያለው ፈርጣማ ወጣት፡፡
‹‹እውነተኛ ስምህ ነው የጠየቅኩህ ?››
‹‹ከማል ነው የምባለው፡፡ ግን በዚህ ስም ከነቤተሰቦቼ በስተቀር ሌላ የሚያውቀኝ ሰው የለም… ሁሉም ባሪያው ነው የሚሉኝ ››
‹‹እሺ አንተስ .. ?››አለው ወደሌለኛው ዞሮ
‹‹ኤልያስ እባላለው››
‹‹እሺ ሳምሶናይቱ ውስጥ ያለው ምንድነው?መቼስ አሁንም ፋይል ነው አትሉኝም?››
‹‹50 ሺ ብር ነው››መለሰ ባሪያው፡፡
‹‹ከየት ነው የመነተፋችሁት? ››
‹‹ከአንድ ሀብታም ነው››
‹‹50 ሺ ብር መሆኑን በምን አወቃችሁ? ቆጥራችሁታል እንዴ?››
‹‹አይ እኛ ወደ ሰራ ከመሰማራታችን በፊት ጥናት አካሂደን ነው ፡፡ይሄ ሰውዬ ትናንት ነው ይሄንን ብር ይዞት ወደ ቤቱ የገባው፡፡ደግሞ ብሩን ሰራ ሰርቶ ወይም ነግዶ ያገኘው አይደለውም ፡፡አንድ የመንግስት ፕሮጀክት ለአንድ ኮንትራክተር በተጭበረበረ ጫረታ እንዲያገኝ ስላደረገው …ከኮንትራክተሩ የተሰጠው ብር ነው፡፡››
‹‹ጥሩ ነው፡፡ ለመሆኑ ብሩን ምን ታረጉታላችሁ?››
‹‹ያው ሁሌ እንደምናደርገው… እኩል እኩል እንካፍለዋለን››ኤልያስ መለሰለት፡፡
‹‹እሺ ያ ማለት ለምሳሌ ለአንተ የደረሰህን ሃያ አምስት ሺ ብር ምን ታርገዋለህ? መቼስ ትንሽ ሚባል ገንዘብ አይደለም?››
‹‹ብዙ ብር ነው እንዴ…?አይመስለኝም፡፡ያው እኔ ሁል ጊዜ እንደማደርገው ዙሪያዬ ካሉ ጀለሶቼ ጋር እንጨፍርበታለን …ለአስራአምስት ቀንም ሆነ ለአንድ ወር ዘና እንልበታለን ››
‹‹በቃ…››
‹‹በቃ››
‹‹ሌላ ምንም ፍላጐት ወይም አላማ የለህም?››
‹‹የለኝም››
‹‹ግን እኮ እንዲህ ባለው አጋጣሚ እንዲህ ጠቀም ያለ ብር ስታገኝ ህይወትህን ለመቀየር ለምን አትጠቀምበትም..?ሁልግዜ ሌባ መሆን ይቅርና ሁል ጊዜ ፖሊስ መሆንም ይሰለቻል››
‹‹አኔ አላማዬ ሌባ ሆኜ አባቴን ማበሳጨት ብቻ ነው፡፡››
‹‹ማለት?››
‹‹ተከብሬበታለው….በሚልበት ከተማ እሱ ልጅ እኮ ሌባ ነው የሚባለውን እየሰማ እንዲሳቀቅ እና እንዲሸማቀቅ ነው ምፈልገው››ብሎ መለሰለት፡፡ገረመው ..ይሄ እንእደሱ በቀል ላይ ያለ ጓረምሳ እንደሆነ ተረዳ፡፡
‹‹አባትህ አበሳጭቶኸል ማለት ነው፡፡?››ይበልጥ እንዲያብራራለት የሰነዘረለት ጥያቄ ነው፡፡
‹‹አበሳጭቶኸል የሚለው አይገልፀውም..አባቴ በገንዘቡ የሚመካ… ሰው ጤፍ የሆነ ዲክታተር ሰው ነው..እኔ ያልኩት ብቻ ካልሆነ ብሎ ጦርነት የሚያስነሳ ..ገንዘብ ስላለው ብቻ የእሱ አመለካከት ገዢ እና ፍጹም እንደሆነ የሚያስብ ነው፡፡እኔ ደግሞ እንደሌሎቹ የቤተሰቦቻችን አባላት ያለውን ሁሉ ዝም ብዬ አልቀበለውም፡፡ያልመሰለኝን ነገር አልመሰለኝም ብዬ እመልስለታለው…ይሄ ደግሞ ያበሳጨዋል፡፡‹….ከዛ የተነሳ ልጄ አይደለህም….. እቤቴን ለቀህ ውጣ› ብሎ አባረረኝ፡፡እኔም አልተለማመጥኩትም …ወጣው፡፡ ከነባርች ጋር ተቀላቀልኩ..ይሄው ይሄንን ስራ ብቻ እየሰራው እኖራለው..እሱን እንኳን ከ5 ጊዜ በላይ ዘርፌዋለው..ከዛ ቡኃላ ሽምግሌ ቢልክብኝ ..ተመልሰህ ወደ ቤት ግባና የፈለግከወን ላድርግልህ ቢለኝ አልሰማውትም..ሊያስፈራራኝም ሊያስደበድበኝም ሞክሮ ነበር፡፡ ግን ይሄውና እኔም እንዳበሳጨውት እሱም እንደተበሳጨብኝ እና እንዳፈረብኝ እዚህቺው ከተማ ውስጥ እየተገፋፋን እንኖራለን፡፡››
‹‹ይገርማል…አንተስ ባሪያው? ››
‹‹የእኔ እንኳን የተለየ ነው››
‹‹እኮ እንዴት እንደሚለይ ንገረኝ››
‹‹ከእኔ ታሪክ አንፃር የኤልያስ ጥጋብ የሚባል ነው፡፡እናቴ እኔ እና ሶስት ወንድሞቼን ቀበሌ 8 አስፓልት ዳር በምትገኝ ባዘመመች የቀበሌ ቤት አረቄ እና ጠላ እየቸረቸረች ታሳድገን ነበር፡፡ብኃላ ግን አንዱ ሀብታም ፎቅ ሊያንጣልልበት ፈለገና ከመዘጋጃው ጋር ስለተስማማ የአካባቢው ጭርንቁስ ቤቶች ሁሉ እንዳለ ተጠራርገው እንዲፈርሱለት ስለተደረገ… የእኛም መጠለያ አብራ የመወገድ እጣ ደረሳት፡፡እኛንም ከከተማወ አውጥተው አሰፈሩን፡፡እናቴ እንዴት አድርጋ እንደምታሳድገን ግራ ገባት፡፡ያለአባት አራት ልጅ ማሳደግ በጣም ከባድ ነበር፡፡እንጀራ እየጋገረች ገባያ ድረስ እየወሰደች ኑሮችንን ለመግፋት ሞከረች …አልቻለችም..፡፡ቡኃላ ተስፋ ቆረጠች መሰለኝ በብስጭት ብዙም ሳትቆይ ድንገት በበሽታ ተመታ ወደቀች …አልተነሳችም ፡፡ሞተች፡፡
ካዛ ያው ታለቅ እኔ ስነበርኩ የወንድሞቼን ሀላፊነት ሳልወድ በግድ ባልፀና ጫንቃዬ ተረከብኩ ፡፡የቀን ስራ እየሰራው የእለት ጉርሳችንን ለማግኘት ጣርኩ..ሲጋራ እና መስቲካ እያዞኩ በመሸጥ ወንድሞቼን ለመቀለብም ሞከርኩ …ግን አርኪ አልነበርም..ቀስ በቀስ ግን በአጋጣሚ በቀረብኮቸው ጓደኞቼ ገፋፊነት ወደ እዚህ ስራ ገባው..አሪፍም ሆነልኝ ፡፡የተሸለ ቤት ተከራይቼ የተሸለ ምግብ በመመገብ ወንድሞቼን ማኖር ጀመርኩ.. ከእናቴ ሞት ብኃላ ያቆረጡትን ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ማድረግ ቻልኩ …ምን አልባት ብታሰር ወይም በዚህ ስራ ላይ አደጋ ቢደርስብኝ ወንድሞቼ መልሰው ወደ እዛ የዘቀጠ ድህነት እንዳይመለሱ ጠርቀም ያለ ብር በባንክ ቤት ላሰቅቀምጥላቸወም ቻልኩ..››
‹‹ይገርማል….ሶስቱንም ወንድሞችህን ታስተምራለህ?››
አዎ እኔ የመማር ዕድሉን ባላገኝም እነሱን ግን በደንብ አስተምራለው፡፡ትንሹ ዘንድሮ ስምንተኛ ክፈል ማትሪክ ይወስዳል..መካከለኛው ፕሪፓራቶሪ ተማሪ ነው፡፡ሌላው ጐንደር ዩኒቨርሲቲ ሶስተኛ አመት የህክምና ተማሪ ሆኖልኛል››
‹‹እየቀለድክ ነው?››
‹‹በፍጹም..የነገርኩህ ሁሉ እውነት ነው››
‹‹ቆይ ወንድሞችህ ይሄንን ስራ እንደምትሰራ ያውቃሉ?››
‹‹አያውቁም..የአየር ባየር ንግድ እየነገድኩ እንደማኖራቸው ነው የሚያውቁት፡፡››
‹‹በጣም ይገርማል …››ብሎ ለደቂቃዎች በጸጥታ ተውጦ ካሰላሰለ ብኃላ‹‹….ከዛሬ ጀምሮ አብረን ነው የምንሰራው››አላቸው፡፡ሁለቱም እስር ቤት ነው ምከታችሁ
:
#ክፍል_ሀያ_አንድ
:
✍ድርሰት:-በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
..ኤልያስ ምላጩን ሳበው …ቀጭ የሚል ድምጽ እንጂ ዷ የሚል ፍንዳታ ወይም ጨኸት አልተሰማም ፡፡ ግራ በመጋት እራሱ ደነገጠ..ተስፋ ባለመቁረጥ ዳግመኛ ሞከረ … መልሶ ምላጩን ሳበው..አሁንም ቀጭ የሚል ተመሳሳይ ድምፅ ነው የተሰማው፡፡
በዚህ ጊዜ ግን ለኤልያስ እንቅስቃሴ ብዙም ትኩረት ሳይሰጥ ኮማንደሩ የያዘውን የውስኪ ጠርሙስ እና ብርጭቆ ጠረጵዛው ላይ አስቀመጠና ከለበሰው የቢጃማ ኪስ ውስጥ አንድ በመጠኗ በጣም አነስተኛ የሆነች ሽጉጥ አወጣና ወደ እነሱ አቅጣጫ አነጣጠረ እና ተኮሰ፡፡ ቷ..የሚል እስደንጋጭ ድምጽ አሰማች ..ሽጉጧ፡፡ ሁለቱም ግራና ቀኝ ፍንችር ብለው ወደቁ ..ሌላ ተመልካች ሰው ቢኖር ኖሮ እንዴት አድርጐ ቢተኩስ እንዴት አድርጎ ቢያነጣጥር ነው በአንድ ተኩስ እና በአንድ ጥይት ሁለቱን ያነጠፋቸው ብሎ ይገረም ነበር፡፡ኩማደሩ ግን ሽጉጡን በግራ እጁ እንደያዘ በቀኝ እጁ የውስኪውን ጠርሙስ አንስቶ በሶስቱም ብርጭቆ ላይ ቀድቶ እስኪያጠናቅቅ ሁለቱም በድንጋጤ በተጋደሙበት እንዳሉ ነበሩ፡፡
‹‹ኸረ ተነሱ ግድግዳው ለተመታው እናንተ ምን አዘረራችሁ?››
በሰመመን ሰሙትና እንደምንም ተነስተው እየተዞዞሩ እራሳቸውን በእርግጥ አለመመታቸውን ለማረጋገጥ ፈተሹ …በአንድነት ወደኃላቸው ዞረው ከጀርባቸው ያለውን ግድግዳ ተመለከቱ …ጥይቷ ግድግዳውን በስታዋለች፡፡
‹‹ቁጭ በሉ..ግን ላስጠንቅሰቃችሁ ከአሁን ቡኃላ ብታበሳጩኝ ግድግዳውን ሳይሆን ግንባራችሁን ነው የምፈረክሰው፡፡›› ፈራ ተባ እያሉ ወደመቀመጫቸው ተመለሱ፡፡ ውስኪ የተቀዳበትን ብርጭቆ አቀበላቸው እና የራሱን ይዞ ተቀመጠ፡፡
‹‹እኔ ካላወቃችሁኝ ኩማንደር መሀሪ እባላለው..የእናንተስ?››
‹‹እኔ ባርያው እባላለው ››አለው ጠቆር ያለው ፈርጣማ ወጣት፡፡
‹‹እውነተኛ ስምህ ነው የጠየቅኩህ ?››
‹‹ከማል ነው የምባለው፡፡ ግን በዚህ ስም ከነቤተሰቦቼ በስተቀር ሌላ የሚያውቀኝ ሰው የለም… ሁሉም ባሪያው ነው የሚሉኝ ››
‹‹እሺ አንተስ .. ?››አለው ወደሌለኛው ዞሮ
‹‹ኤልያስ እባላለው››
‹‹እሺ ሳምሶናይቱ ውስጥ ያለው ምንድነው?መቼስ አሁንም ፋይል ነው አትሉኝም?››
‹‹50 ሺ ብር ነው››መለሰ ባሪያው፡፡
‹‹ከየት ነው የመነተፋችሁት? ››
‹‹ከአንድ ሀብታም ነው››
‹‹50 ሺ ብር መሆኑን በምን አወቃችሁ? ቆጥራችሁታል እንዴ?››
‹‹አይ እኛ ወደ ሰራ ከመሰማራታችን በፊት ጥናት አካሂደን ነው ፡፡ይሄ ሰውዬ ትናንት ነው ይሄንን ብር ይዞት ወደ ቤቱ የገባው፡፡ደግሞ ብሩን ሰራ ሰርቶ ወይም ነግዶ ያገኘው አይደለውም ፡፡አንድ የመንግስት ፕሮጀክት ለአንድ ኮንትራክተር በተጭበረበረ ጫረታ እንዲያገኝ ስላደረገው …ከኮንትራክተሩ የተሰጠው ብር ነው፡፡››
‹‹ጥሩ ነው፡፡ ለመሆኑ ብሩን ምን ታረጉታላችሁ?››
‹‹ያው ሁሌ እንደምናደርገው… እኩል እኩል እንካፍለዋለን››ኤልያስ መለሰለት፡፡
‹‹እሺ ያ ማለት ለምሳሌ ለአንተ የደረሰህን ሃያ አምስት ሺ ብር ምን ታርገዋለህ? መቼስ ትንሽ ሚባል ገንዘብ አይደለም?››
‹‹ብዙ ብር ነው እንዴ…?አይመስለኝም፡፡ያው እኔ ሁል ጊዜ እንደማደርገው ዙሪያዬ ካሉ ጀለሶቼ ጋር እንጨፍርበታለን …ለአስራአምስት ቀንም ሆነ ለአንድ ወር ዘና እንልበታለን ››
‹‹በቃ…››
‹‹በቃ››
‹‹ሌላ ምንም ፍላጐት ወይም አላማ የለህም?››
‹‹የለኝም››
‹‹ግን እኮ እንዲህ ባለው አጋጣሚ እንዲህ ጠቀም ያለ ብር ስታገኝ ህይወትህን ለመቀየር ለምን አትጠቀምበትም..?ሁልግዜ ሌባ መሆን ይቅርና ሁል ጊዜ ፖሊስ መሆንም ይሰለቻል››
‹‹አኔ አላማዬ ሌባ ሆኜ አባቴን ማበሳጨት ብቻ ነው፡፡››
‹‹ማለት?››
‹‹ተከብሬበታለው….በሚልበት ከተማ እሱ ልጅ እኮ ሌባ ነው የሚባለውን እየሰማ እንዲሳቀቅ እና እንዲሸማቀቅ ነው ምፈልገው››ብሎ መለሰለት፡፡ገረመው ..ይሄ እንእደሱ በቀል ላይ ያለ ጓረምሳ እንደሆነ ተረዳ፡፡
‹‹አባትህ አበሳጭቶኸል ማለት ነው፡፡?››ይበልጥ እንዲያብራራለት የሰነዘረለት ጥያቄ ነው፡፡
‹‹አበሳጭቶኸል የሚለው አይገልፀውም..አባቴ በገንዘቡ የሚመካ… ሰው ጤፍ የሆነ ዲክታተር ሰው ነው..እኔ ያልኩት ብቻ ካልሆነ ብሎ ጦርነት የሚያስነሳ ..ገንዘብ ስላለው ብቻ የእሱ አመለካከት ገዢ እና ፍጹም እንደሆነ የሚያስብ ነው፡፡እኔ ደግሞ እንደሌሎቹ የቤተሰቦቻችን አባላት ያለውን ሁሉ ዝም ብዬ አልቀበለውም፡፡ያልመሰለኝን ነገር አልመሰለኝም ብዬ እመልስለታለው…ይሄ ደግሞ ያበሳጨዋል፡፡‹….ከዛ የተነሳ ልጄ አይደለህም….. እቤቴን ለቀህ ውጣ› ብሎ አባረረኝ፡፡እኔም አልተለማመጥኩትም …ወጣው፡፡ ከነባርች ጋር ተቀላቀልኩ..ይሄው ይሄንን ስራ ብቻ እየሰራው እኖራለው..እሱን እንኳን ከ5 ጊዜ በላይ ዘርፌዋለው..ከዛ ቡኃላ ሽምግሌ ቢልክብኝ ..ተመልሰህ ወደ ቤት ግባና የፈለግከወን ላድርግልህ ቢለኝ አልሰማውትም..ሊያስፈራራኝም ሊያስደበድበኝም ሞክሮ ነበር፡፡ ግን ይሄውና እኔም እንዳበሳጨውት እሱም እንደተበሳጨብኝ እና እንዳፈረብኝ እዚህቺው ከተማ ውስጥ እየተገፋፋን እንኖራለን፡፡››
‹‹ይገርማል…አንተስ ባሪያው? ››
‹‹የእኔ እንኳን የተለየ ነው››
‹‹እኮ እንዴት እንደሚለይ ንገረኝ››
‹‹ከእኔ ታሪክ አንፃር የኤልያስ ጥጋብ የሚባል ነው፡፡እናቴ እኔ እና ሶስት ወንድሞቼን ቀበሌ 8 አስፓልት ዳር በምትገኝ ባዘመመች የቀበሌ ቤት አረቄ እና ጠላ እየቸረቸረች ታሳድገን ነበር፡፡ብኃላ ግን አንዱ ሀብታም ፎቅ ሊያንጣልልበት ፈለገና ከመዘጋጃው ጋር ስለተስማማ የአካባቢው ጭርንቁስ ቤቶች ሁሉ እንዳለ ተጠራርገው እንዲፈርሱለት ስለተደረገ… የእኛም መጠለያ አብራ የመወገድ እጣ ደረሳት፡፡እኛንም ከከተማወ አውጥተው አሰፈሩን፡፡እናቴ እንዴት አድርጋ እንደምታሳድገን ግራ ገባት፡፡ያለአባት አራት ልጅ ማሳደግ በጣም ከባድ ነበር፡፡እንጀራ እየጋገረች ገባያ ድረስ እየወሰደች ኑሮችንን ለመግፋት ሞከረች …አልቻለችም..፡፡ቡኃላ ተስፋ ቆረጠች መሰለኝ በብስጭት ብዙም ሳትቆይ ድንገት በበሽታ ተመታ ወደቀች …አልተነሳችም ፡፡ሞተች፡፡
ካዛ ያው ታለቅ እኔ ስነበርኩ የወንድሞቼን ሀላፊነት ሳልወድ በግድ ባልፀና ጫንቃዬ ተረከብኩ ፡፡የቀን ስራ እየሰራው የእለት ጉርሳችንን ለማግኘት ጣርኩ..ሲጋራ እና መስቲካ እያዞኩ በመሸጥ ወንድሞቼን ለመቀለብም ሞከርኩ …ግን አርኪ አልነበርም..ቀስ በቀስ ግን በአጋጣሚ በቀረብኮቸው ጓደኞቼ ገፋፊነት ወደ እዚህ ስራ ገባው..አሪፍም ሆነልኝ ፡፡የተሸለ ቤት ተከራይቼ የተሸለ ምግብ በመመገብ ወንድሞቼን ማኖር ጀመርኩ.. ከእናቴ ሞት ብኃላ ያቆረጡትን ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ማድረግ ቻልኩ …ምን አልባት ብታሰር ወይም በዚህ ስራ ላይ አደጋ ቢደርስብኝ ወንድሞቼ መልሰው ወደ እዛ የዘቀጠ ድህነት እንዳይመለሱ ጠርቀም ያለ ብር በባንክ ቤት ላሰቅቀምጥላቸወም ቻልኩ..››
‹‹ይገርማል….ሶስቱንም ወንድሞችህን ታስተምራለህ?››
አዎ እኔ የመማር ዕድሉን ባላገኝም እነሱን ግን በደንብ አስተምራለው፡፡ትንሹ ዘንድሮ ስምንተኛ ክፈል ማትሪክ ይወስዳል..መካከለኛው ፕሪፓራቶሪ ተማሪ ነው፡፡ሌላው ጐንደር ዩኒቨርሲቲ ሶስተኛ አመት የህክምና ተማሪ ሆኖልኛል››
‹‹እየቀለድክ ነው?››
‹‹በፍጹም..የነገርኩህ ሁሉ እውነት ነው››
‹‹ቆይ ወንድሞችህ ይሄንን ስራ እንደምትሰራ ያውቃሉ?››
‹‹አያውቁም..የአየር ባየር ንግድ እየነገድኩ እንደማኖራቸው ነው የሚያውቁት፡፡››
‹‹በጣም ይገርማል …››ብሎ ለደቂቃዎች በጸጥታ ተውጦ ካሰላሰለ ብኃላ‹‹….ከዛሬ ጀምሮ አብረን ነው የምንሰራው››አላቸው፡፡ሁለቱም እስር ቤት ነው ምከታችሁ
👍2
ያላቸው ያህል ነው የተደናገጡት..መደናገጥም ብቻ ሳይሆን ጆሮአቸውንም ጭምር ነው የተጠራጠሩት
‹‹ይቅርታ ኩማንደር… አልሰማንህም››አለው ኤልያስ
‹‹አብረን ነው የምንሰራው ..አየህ አንተ ይህን ስራ የምትሰራው አባትህን ለማበሳጨት ነው …ባሪያው ደግሞ ወንድሞቹን አስተምሮ ጥሩ ደረጃ ለማድረስ ነው..እኔም የራሴ የሆነ ዓላማ አለኝ..ማንኛውንም ስራ ከመስራታችሁ በፊት ጥናታችሁን ወደተግባር ከመቀየራችሁ በፊት እንማከርበትና ወይ እናፀድቀውና
እንድትገብሩት እናሳልፈዋለን ወይም እንሽረዋለን..እኔም በእኔ በኩል እንዲሰሩልኝ የምፍልጋቸው ስራዎች ይኖሩኛል..ምን ይመስላችሆል?››
‹፣እንዴ ኩማደር!!! የእውነትህን ከሆነ ለእኛ ይሄ ታላቅ እድል ነው››አለ ባሪያው
‹‹እሺ ኤልያስስ?›››
‹‹እንዴት ያለ ቀሽት ስራ እንደምንሰራ እያታሰበኝ ከአሁኑ ውስጤ በደስታ እየተፍነከነከ ነው››
‹‹እንግዲያው ጥሩ ከዛሬ ጀምሮ እኛ ሶስታችን ሚስጥራዊ አጋሮች ሆነናል..ታዲያ ይሄ ሚስጥር ከሶስታችን ውጭ አንድ ሰው ጆሮ ቢገባ ስቃዩ በእናንተ ይብሳል›› አስጠነቀቃቸው፡፡
‹‹ኸረ እርስ በርሳችን እራሱ ስለዚህ ጉዳይ አንተ በሌለህበት አናወራም››በማለት ሚስጥሩ እንደተጠበቀ እንደሚቆይ ባሪያው አረጋገጠለት…. ኤልስም በግንባር ንቅንቅታ መስማማቱን ገለጸ..
‹‹እንግዲያው ከመንጋቱ በፊት ትንሽ አረፍ ማለት ስላለብን ከፈላጋችሁ እዚሁ ሶፋ ላይ አረፍ በሉ ወደቤት እንሄዳለን የምትሉ ከሆነም መልካም መንገድ››
‹‹ብንሄድ ይሻላል››አለ ባሪያው ፈጥኖ ባለማመን
‹‹እሺ እንደፈለጋችሁ››ብሎ ተነስቶ የተቆለፈውን በራፍ ከፈተላቸው..ባለማመን እርስ በርስ ተያዘው እየታከኩ ወጡ
‹‹እንዴ ቆይ እንጂ››አለ ኩማደር፡፡ደግሞ ምን ሊለን ነው ብለው ባሉበት ተገትረው ቆሙ ፡፡ ጠረጵዛው ስር ያለውን ሳምሶናይት አነሳና ‹‹እቃችውን እረስታችሁ ሄዳችሁ እኮ !!!›› ብሎ አቀበላቸውና ወደ ውስጥ ተመልሶ በራፉን ቆልፎ ወደ መኝታ ቤት ገባ…
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
እሁድ.. እለተ-ሰንበት አካልም መንፈስም እፎይታ የሚያገኝበት እለት ነች… ዘመድ ከዘመዱ የሚጠያየቅበት… ወዳጅ ከወዳጁ የሚደዋወሉበት… ፍቅረኛ ከፍቅረኛ የሚገናኝበት… የተራራቀ የሚቀራረብበት ቅዱስ የተባለች የእርጋታ ቀን ፡፡
የሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቅጥር ግቢ ነጭ በነጭ በለበሱ ህዝበ ክርስቲያን ተጣቧል፡፡ሁሉም ባሉበት ቦታ በመቆም ስርዓተ ቅዳሴውን በጽሞና ይከታተላሉ..መንፈሱን ወደ ቤቱ.. ወደ ገዛ ችግሩ እየሮጠ የሚያስቸግረው አንዳንድ ያልተረጋጋ ምዕመንም እንደምንም እራሱን ለመቆጣጠር በመሞከር በቆመበት ይቁነጠነጣል፡፡
ከለሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ለፈጣሪያቸው ውዳሴ ማቅረብ የጀመሩት ካህናት ከጥዋቱ ሁለት ሰዓት ተኩል ሲሆን ተልዕኮቸውን አጠናቆቁ..ከዛም ብራኬና የጠበል እደላው ፕሮግራም መካሄድ ጀመረ፡፡ ህዘብ በጣም ብዛት ያለው ስለሆነ የካህኑን እጅ ለመሳለም አንዱ በአንዱ ላይ እየወጣ ይተረማመስ ነበር …እንደምንም ተሳክቶለት ከተሳለመ ብኃላ ወደ ጠበሉ ይሄዳ ፡፡ጠበሉን ብዛት ያላቸው ዲያቆኖች በባልዲ በመያዝ ሰው በተቀመጠበት እየተዘዋወሩ ነው የሚያድሉት፡፡
ከደቂቃዎች ቡኃላ የጠበል ዕደላው ፕሮግራም ተጠናቀቀ፡፡አንድ ጥቁር ቀሚስ የለበሰ ወጣት ሰባኪ ጥቁር ልባስ ያለውን መጽሀፍ ቁዱሱን በቀኝ እጁ ይዞ ወደ መድረኩ በመውጣት ጉሮሮውን አጸዳዳ፡፡በሚስረቀረቅ ተስገምጋሚ ድምጽ ስብከቱን ማሰማት ጀመረ.. ምዕመናኑ በጠቅላላ ባሉበት ተረጋግተው ስብከቱን በጽሞና እየተከታተሉ ነው፡፡ከወጣቱ አንደበት የሚፈልቁ ዓረፍተነገሮች በአማረኛ ቋንቋ የታንቆለጳጰሱ ከማጽናናት እና ተስፋ ከማስጨበጥ ይልቅ የሚያስፈራሩ እና የሚያርዱ ናቸው፡፡ስለእየሱስ ክርስቶስ መምጫ ቀን (ስለእለተ ምጽአት) ነው ስብከቱ፡
፡‹መንግስ-ተሰማያት ቀርባለች እና በወንጌል አምናችሁ ንሰሀ ግቡ..ብኃላ ለቅሶ እና ጥርስ ማፎጨት እንዳይሆንባችሁ ከአሁኑ ተዘጋጁ..በንሰሀ ታጠቡ..ተንኮል ምቀኝነት አስወግዱ ..አልያ እሳቱ ከማይጠፋበት ትሎቹ ወደማያንቀላፉበት ዘላለማዊ ገሀነም መጣል ይሆናል እጣ ክፍላችሁ…ከሞት ቡኃላ ስለለው ነፍሳችሁ እጣፋንታ ተጨነቁ..አለም አላፊና ጠፊ ነች…ሰጋም ረጋፊ ነች..ነፍስ ግን ወደዘላለማዊነት ትሸጋገራለች……….. ››እያለ መጽሀፍ ቅዱስ የሚያግዘው መረጃ ምዕራፍ እና ቁጥር እየጠቀሰ ለ40 ደቂቃ ስብከቱን ሰበከ እና አጠናቀቀ…ግን አሳርጐ መድረኩን ከመልቀቁ በፊት የተወሰኑ ማሳሰቢያዎች አሉኝ በማለት አንድ ሁለት መልዕክቶችን ከስተላለፈ ቡኃላ‹ ሶስተኛውን ማሳሰቢያ አባታችን ይናገሩልናል› በማለት መድረኩን በቅርብ እርቀት ለሚገኙት አባ ሽፍንፍን ለቀቀላቸው፡፡
አባ ሽፍንፍን ከተቀመጡበት ተነስተው ወደመድረኩ በማምራት ማይኩን በቀኝ እጃቸው ጨበጡና መናገር ጀመሩ፡፡አለባበሳቸው ያው እንደዘወትሩ የተሸፋፈነ እና መላ አካለቸውን የከለለ ነው፡፡ቤተክርሰቲያኑ ቅፅር ግቢ የሚገኙ ምዕመናኖች በአጠቃላይ ከእሳቸው አንደበት የሚነገረውን መልዕክት ለማዳመጥ ከበፊት ይበልጥ ነቃ ነቃ አሉ፡፡ እሷቸውም የወርቅ ቅብ መስቀላቸውን አውጥተው ካማተቡ ቡኃላ ለህዝቡ ሰላምታ አቅርበው ንግግራቸውን እንዲህ ሲሉ ቀጠሉ….
‹‹እንግዲህ የተወደዳችሁ ምዕመናን ምን ጊዜም አንድ ሰው አንድ ነው… ብቻውን ምንም ተዐምር ሊፈጥር አይቻለውም፡፡ ህብረት ካለ ግን የማይቻል ነገር.. የማይተገበር ተአምር የለም፡፡በተለይ እኛ ክርስትያኖች ነን የምንል ክርስቲያኖች መሆናችንን በስም ብቻ ሳይሆን በተግባርም ማሳየት አለብን ብዬ አምናለው፡፡ አሁን ወንድማችን በስብከቱ እንዳስገነዘበን ጌታ በፍርድ ዘመን ሲመጣ ተርቤ አብልታችሁኛል? ታርዤ አልብሳችሁኛል? ታስሬ ጠይቃችሁኛል? ብሎ ጥያቄ ሲያቀርብልን ጌታ ሆይ መች መጥተህ እንዲህ አድርጉልኝ አልከንና ?ብለን መልሰን እንጠይው ይሆናል….ግን ይሄ የሚያዋጣ አይመስለኝም፡፡
ምክንያቱም እዚሁ የቤተክርስቲያናችንን አጥር ከበው የሚኖሩ ምንዱባን የእግዚያብሄር ወኪሎች ናቸው …እነሱን ሲበርዳቸው እግዚያብሄርንም እንደሚበርደው ማሰብ አለብን..ሲራቡም እግዚያብሄር እንደሚራብ መዘንጋት የለብንም..፡፡አንድ ቀን እነሱን ምሳ አበላን ማለት አንድ ቀን እግዚያብሁርን እንደጋበዘንው መቁጠር አለብን፡፡ይህ ሁሉ ክርሰቲያን ይሄ ሁሉ ምዕመን እያለ እንዴት ነው ይሄ ሁሉ የእኔ ቢጤ ቤተክርስቲያናችንን ከቦ በብርድና በፀሀይ እየተንቃቃ ከሰዋዊነት በታች ዝቅ ብሎ የሚኖረው? ለመሆኑ ሁላችንም ብንተባበር አንድ ችግረኛ ለመቶ ምዕመናን ይደርሳልን? አይመስለኝም፡፡
በአጭሩ እኔ ለማት የፈለግኩት ብዙዎቻችሁ እንደምታውቁት በከተማችን ውስጥ በችግር የሚማቅቁትን ወገኖቻንን ለመርዳት ትንሽ ሙከራ ለማድረግ እየሞከርኩ ነው፡፡እነዚህ ድሆች በምፅዋት ገንዘብ የእለት ጉርሳቸውን አግኝተው እንዲኖሩ ብቻ ሳይሆን እራሳቸውን ቀስ በቀስ የሚችሉበት ሁኔታ ማመቻቸት ነው እቅዴ…ሁሉም እንደየ አቅሙ እና እንደየ ችሎታው የሆነች ነገር መስራትና ከዛች በሚያገኘው ገንዘብ መኖር እንዲችል ማገዝ ነው ህልሜ.. ለዚህም ተግባር የሚንቀሳቀስ በቤተክርስቲያናችን ስም አንድ ጎዳናዎች የሰው ጅ መመላለሻዎች እንጂ መኖሪያ መሆን የለባቸውም ›በሚል መሪ ቃል የሚንቀሳቀስ ማህበር በማቋቋም በተቀናጀ መልኩ እርዳታ የሚያሰባስብ እና እቅዱን ወደተግባር የሚተረጉም ከህዝበ ክርስቲያኑ የተመረጠ አንድ ኮሚቴ እንዲቋቋም ከሰበካ ጉባዬው ፍቃድ ስላገኘን በዚህ ጉዳይ ላይ ህዝብ አስተያያት እንዲሰጥበት እና ኮሚቴዎችን እንዲመርጥልኝ እና እስከመጨረሻውም ከጐናችን እንዲሆን ለመጠየቅ ነው ፊታችሁ የቆምኩት፡፡
‹‹ይቅርታ ኩማንደር… አልሰማንህም››አለው ኤልያስ
‹‹አብረን ነው የምንሰራው ..አየህ አንተ ይህን ስራ የምትሰራው አባትህን ለማበሳጨት ነው …ባሪያው ደግሞ ወንድሞቹን አስተምሮ ጥሩ ደረጃ ለማድረስ ነው..እኔም የራሴ የሆነ ዓላማ አለኝ..ማንኛውንም ስራ ከመስራታችሁ በፊት ጥናታችሁን ወደተግባር ከመቀየራችሁ በፊት እንማከርበትና ወይ እናፀድቀውና
እንድትገብሩት እናሳልፈዋለን ወይም እንሽረዋለን..እኔም በእኔ በኩል እንዲሰሩልኝ የምፍልጋቸው ስራዎች ይኖሩኛል..ምን ይመስላችሆል?››
‹፣እንዴ ኩማደር!!! የእውነትህን ከሆነ ለእኛ ይሄ ታላቅ እድል ነው››አለ ባሪያው
‹‹እሺ ኤልያስስ?›››
‹‹እንዴት ያለ ቀሽት ስራ እንደምንሰራ እያታሰበኝ ከአሁኑ ውስጤ በደስታ እየተፍነከነከ ነው››
‹‹እንግዲያው ጥሩ ከዛሬ ጀምሮ እኛ ሶስታችን ሚስጥራዊ አጋሮች ሆነናል..ታዲያ ይሄ ሚስጥር ከሶስታችን ውጭ አንድ ሰው ጆሮ ቢገባ ስቃዩ በእናንተ ይብሳል›› አስጠነቀቃቸው፡፡
‹‹ኸረ እርስ በርሳችን እራሱ ስለዚህ ጉዳይ አንተ በሌለህበት አናወራም››በማለት ሚስጥሩ እንደተጠበቀ እንደሚቆይ ባሪያው አረጋገጠለት…. ኤልስም በግንባር ንቅንቅታ መስማማቱን ገለጸ..
‹‹እንግዲያው ከመንጋቱ በፊት ትንሽ አረፍ ማለት ስላለብን ከፈላጋችሁ እዚሁ ሶፋ ላይ አረፍ በሉ ወደቤት እንሄዳለን የምትሉ ከሆነም መልካም መንገድ››
‹‹ብንሄድ ይሻላል››አለ ባሪያው ፈጥኖ ባለማመን
‹‹እሺ እንደፈለጋችሁ››ብሎ ተነስቶ የተቆለፈውን በራፍ ከፈተላቸው..ባለማመን እርስ በርስ ተያዘው እየታከኩ ወጡ
‹‹እንዴ ቆይ እንጂ››አለ ኩማደር፡፡ደግሞ ምን ሊለን ነው ብለው ባሉበት ተገትረው ቆሙ ፡፡ ጠረጵዛው ስር ያለውን ሳምሶናይት አነሳና ‹‹እቃችውን እረስታችሁ ሄዳችሁ እኮ !!!›› ብሎ አቀበላቸውና ወደ ውስጥ ተመልሶ በራፉን ቆልፎ ወደ መኝታ ቤት ገባ…
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
እሁድ.. እለተ-ሰንበት አካልም መንፈስም እፎይታ የሚያገኝበት እለት ነች… ዘመድ ከዘመዱ የሚጠያየቅበት… ወዳጅ ከወዳጁ የሚደዋወሉበት… ፍቅረኛ ከፍቅረኛ የሚገናኝበት… የተራራቀ የሚቀራረብበት ቅዱስ የተባለች የእርጋታ ቀን ፡፡
የሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቅጥር ግቢ ነጭ በነጭ በለበሱ ህዝበ ክርስቲያን ተጣቧል፡፡ሁሉም ባሉበት ቦታ በመቆም ስርዓተ ቅዳሴውን በጽሞና ይከታተላሉ..መንፈሱን ወደ ቤቱ.. ወደ ገዛ ችግሩ እየሮጠ የሚያስቸግረው አንዳንድ ያልተረጋጋ ምዕመንም እንደምንም እራሱን ለመቆጣጠር በመሞከር በቆመበት ይቁነጠነጣል፡፡
ከለሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ለፈጣሪያቸው ውዳሴ ማቅረብ የጀመሩት ካህናት ከጥዋቱ ሁለት ሰዓት ተኩል ሲሆን ተልዕኮቸውን አጠናቆቁ..ከዛም ብራኬና የጠበል እደላው ፕሮግራም መካሄድ ጀመረ፡፡ ህዘብ በጣም ብዛት ያለው ስለሆነ የካህኑን እጅ ለመሳለም አንዱ በአንዱ ላይ እየወጣ ይተረማመስ ነበር …እንደምንም ተሳክቶለት ከተሳለመ ብኃላ ወደ ጠበሉ ይሄዳ ፡፡ጠበሉን ብዛት ያላቸው ዲያቆኖች በባልዲ በመያዝ ሰው በተቀመጠበት እየተዘዋወሩ ነው የሚያድሉት፡፡
ከደቂቃዎች ቡኃላ የጠበል ዕደላው ፕሮግራም ተጠናቀቀ፡፡አንድ ጥቁር ቀሚስ የለበሰ ወጣት ሰባኪ ጥቁር ልባስ ያለውን መጽሀፍ ቁዱሱን በቀኝ እጁ ይዞ ወደ መድረኩ በመውጣት ጉሮሮውን አጸዳዳ፡፡በሚስረቀረቅ ተስገምጋሚ ድምጽ ስብከቱን ማሰማት ጀመረ.. ምዕመናኑ በጠቅላላ ባሉበት ተረጋግተው ስብከቱን በጽሞና እየተከታተሉ ነው፡፡ከወጣቱ አንደበት የሚፈልቁ ዓረፍተነገሮች በአማረኛ ቋንቋ የታንቆለጳጰሱ ከማጽናናት እና ተስፋ ከማስጨበጥ ይልቅ የሚያስፈራሩ እና የሚያርዱ ናቸው፡፡ስለእየሱስ ክርስቶስ መምጫ ቀን (ስለእለተ ምጽአት) ነው ስብከቱ፡
፡‹መንግስ-ተሰማያት ቀርባለች እና በወንጌል አምናችሁ ንሰሀ ግቡ..ብኃላ ለቅሶ እና ጥርስ ማፎጨት እንዳይሆንባችሁ ከአሁኑ ተዘጋጁ..በንሰሀ ታጠቡ..ተንኮል ምቀኝነት አስወግዱ ..አልያ እሳቱ ከማይጠፋበት ትሎቹ ወደማያንቀላፉበት ዘላለማዊ ገሀነም መጣል ይሆናል እጣ ክፍላችሁ…ከሞት ቡኃላ ስለለው ነፍሳችሁ እጣፋንታ ተጨነቁ..አለም አላፊና ጠፊ ነች…ሰጋም ረጋፊ ነች..ነፍስ ግን ወደዘላለማዊነት ትሸጋገራለች……….. ››እያለ መጽሀፍ ቅዱስ የሚያግዘው መረጃ ምዕራፍ እና ቁጥር እየጠቀሰ ለ40 ደቂቃ ስብከቱን ሰበከ እና አጠናቀቀ…ግን አሳርጐ መድረኩን ከመልቀቁ በፊት የተወሰኑ ማሳሰቢያዎች አሉኝ በማለት አንድ ሁለት መልዕክቶችን ከስተላለፈ ቡኃላ‹ ሶስተኛውን ማሳሰቢያ አባታችን ይናገሩልናል› በማለት መድረኩን በቅርብ እርቀት ለሚገኙት አባ ሽፍንፍን ለቀቀላቸው፡፡
አባ ሽፍንፍን ከተቀመጡበት ተነስተው ወደመድረኩ በማምራት ማይኩን በቀኝ እጃቸው ጨበጡና መናገር ጀመሩ፡፡አለባበሳቸው ያው እንደዘወትሩ የተሸፋፈነ እና መላ አካለቸውን የከለለ ነው፡፡ቤተክርሰቲያኑ ቅፅር ግቢ የሚገኙ ምዕመናኖች በአጠቃላይ ከእሳቸው አንደበት የሚነገረውን መልዕክት ለማዳመጥ ከበፊት ይበልጥ ነቃ ነቃ አሉ፡፡ እሷቸውም የወርቅ ቅብ መስቀላቸውን አውጥተው ካማተቡ ቡኃላ ለህዝቡ ሰላምታ አቅርበው ንግግራቸውን እንዲህ ሲሉ ቀጠሉ….
‹‹እንግዲህ የተወደዳችሁ ምዕመናን ምን ጊዜም አንድ ሰው አንድ ነው… ብቻውን ምንም ተዐምር ሊፈጥር አይቻለውም፡፡ ህብረት ካለ ግን የማይቻል ነገር.. የማይተገበር ተአምር የለም፡፡በተለይ እኛ ክርስትያኖች ነን የምንል ክርስቲያኖች መሆናችንን በስም ብቻ ሳይሆን በተግባርም ማሳየት አለብን ብዬ አምናለው፡፡ አሁን ወንድማችን በስብከቱ እንዳስገነዘበን ጌታ በፍርድ ዘመን ሲመጣ ተርቤ አብልታችሁኛል? ታርዤ አልብሳችሁኛል? ታስሬ ጠይቃችሁኛል? ብሎ ጥያቄ ሲያቀርብልን ጌታ ሆይ መች መጥተህ እንዲህ አድርጉልኝ አልከንና ?ብለን መልሰን እንጠይው ይሆናል….ግን ይሄ የሚያዋጣ አይመስለኝም፡፡
ምክንያቱም እዚሁ የቤተክርስቲያናችንን አጥር ከበው የሚኖሩ ምንዱባን የእግዚያብሄር ወኪሎች ናቸው …እነሱን ሲበርዳቸው እግዚያብሄርንም እንደሚበርደው ማሰብ አለብን..ሲራቡም እግዚያብሄር እንደሚራብ መዘንጋት የለብንም..፡፡አንድ ቀን እነሱን ምሳ አበላን ማለት አንድ ቀን እግዚያብሁርን እንደጋበዘንው መቁጠር አለብን፡፡ይህ ሁሉ ክርሰቲያን ይሄ ሁሉ ምዕመን እያለ እንዴት ነው ይሄ ሁሉ የእኔ ቢጤ ቤተክርስቲያናችንን ከቦ በብርድና በፀሀይ እየተንቃቃ ከሰዋዊነት በታች ዝቅ ብሎ የሚኖረው? ለመሆኑ ሁላችንም ብንተባበር አንድ ችግረኛ ለመቶ ምዕመናን ይደርሳልን? አይመስለኝም፡፡
በአጭሩ እኔ ለማት የፈለግኩት ብዙዎቻችሁ እንደምታውቁት በከተማችን ውስጥ በችግር የሚማቅቁትን ወገኖቻንን ለመርዳት ትንሽ ሙከራ ለማድረግ እየሞከርኩ ነው፡፡እነዚህ ድሆች በምፅዋት ገንዘብ የእለት ጉርሳቸውን አግኝተው እንዲኖሩ ብቻ ሳይሆን እራሳቸውን ቀስ በቀስ የሚችሉበት ሁኔታ ማመቻቸት ነው እቅዴ…ሁሉም እንደየ አቅሙ እና እንደየ ችሎታው የሆነች ነገር መስራትና ከዛች በሚያገኘው ገንዘብ መኖር እንዲችል ማገዝ ነው ህልሜ.. ለዚህም ተግባር የሚንቀሳቀስ በቤተክርስቲያናችን ስም አንድ ጎዳናዎች የሰው ጅ መመላለሻዎች እንጂ መኖሪያ መሆን የለባቸውም ›በሚል መሪ ቃል የሚንቀሳቀስ ማህበር በማቋቋም በተቀናጀ መልኩ እርዳታ የሚያሰባስብ እና እቅዱን ወደተግባር የሚተረጉም ከህዝበ ክርስቲያኑ የተመረጠ አንድ ኮሚቴ እንዲቋቋም ከሰበካ ጉባዬው ፍቃድ ስላገኘን በዚህ ጉዳይ ላይ ህዝብ አስተያያት እንዲሰጥበት እና ኮሚቴዎችን እንዲመርጥልኝ እና እስከመጨረሻውም ከጐናችን እንዲሆን ለመጠየቅ ነው ፊታችሁ የቆምኩት፡፡
❤1👍1
ብለው እጃቸውን ለአስተያት ከቀሰሩ ሰዎች መካከል እየመረጡ እንዲናገሩ እድል መስጠት ጀመሩ..ለመጀመሪያ ጊዜ የመናገሩን እድል የሰጡት አንድ ጠና ላሉ እራሰ በረሀ ሰውዬ ነው፡፡
‹‹ይህ በጣም ጥሩ እና ከቅድስ ሰው የመነጨ ቅድስ ሀሳብ ነው፡፡ሁሉም የሻሸመኔ ምዕመን ባለው አቅም ይህን ዕቅዶትን ወደ ተግባር ለመቀየር እጁን ከመዘርጋ ወደ ኃላ አይልም..›› ብለው ንግግራቸውን በአጭር አጠናቀው፡ምዕመኑ በዕልልታ ደገፋቸው፡፡ተናጋሪውም ወደ መቀመጫቸው ተመለሱ፡፡
አሁንም ሌሎች ብዙ እጆች ተቀስረው ይታያሉ፡፡ብዙዎቹ የመናገር እድል ተሰጣቸው ሁሉም አቀራረብ ይለያይ እንጂ ተመሳሳይ የድጋፍ እና የአድናቆት ንግግራቸውን ነው ያሰሙት፡፡ከዛ ወደ ኮሚቴ መረጣው ተካሄደ በዚህ ኮሚቴ ውስጥ የተካከተቱት አምሰት ግለሳቦች ሲሆኑ ከአባ ሽፍንፍን በስተቀር ሁሉም በከተማዋ ዲታ የሚባሉ ግለሰቦች ናቸው፡፡አቶ ዳዊት ይግዛው..ወይዘሮ አረገዱ ይመር..አቶ ገመዳ ነገኦ እቶ ወርቅ አለማው እና አባ ሽፍንፍን ናቸው ፡፡
እስቲ ስለእነዚህ ኮሚቴዎች ዘርዘር ያለ ነገር እናውራ፡፡አምስቱም የተከበሩ የከተማዋ ሚሊዬነሮች ናቸው ብለን ተነጋግረናል፡፡ካሰቡበት እና ‹ከልብ ካለቀሱ እንባ አይገድም እንደሚባለው› ከምዕመኑ ሽራፊ ሳበራ ሳንቲም ሳይቀበሉ በቂ የሚባል ገንዘብ ማዋጣት እና የአባ ሽፍንፍንን ፕሮጀክት ወደ ተግባር የመቀየር ብቃትም አቅምም አላቸው፡፡
አቶ ዳዊት ይግዛው በከተማዋ ውስጥ ሁለት ትላልቅ ፋርማሲዎች ያሏቸው ሲሆን ዋና ስራቸው ግን በድብቅ በኬኒያ በኩል በህወጥ መንገድ የተለያዩ መድሀኒቶችን በማስገባት ለጠቅላላ ደቡባዊ የሀገሪቱ ክፍሎች እጥፍ በሆነ ትርፍ ማከፋፈል ነው፡፡ያም ነው ሚሊዬነር ያደረጋቸው፡፡እኚ ሰውዬ የአቶ ወርቅ አለማው የቅርብ ጓደኛ ናቸው..አብዛኛውን ስራዎቻቸውን አብረው ነው የሚሰሩት ፡፡
ወርቅ አለማው ማለት ደግሞ ማን እንደሆነ ሁላችሁም ታውቁታላችሁ፡፡ የኩማደር መሀሪ የቀድሞ እንጀራ አባት ነው፡፡በተጨማሪም የዚህ ኮሚቴም አንዱ አባል ነው፡፡
ሌላዋ የኮሚቴ አባል ወይዘሮ አረገዱ ናቸው..ምን አልባት እዚህ ኮሚቴ ውስጥ በሰውኛ ሚዛን ሲመዘኑ እዚህ ቤተክርስቲያን ቆመው ማምለካቸውና ማስቀደሳቸው ለይስሙላ እና ለታይታ አይደለም ምግባራቸውና እምነታቸው ተቀራራቢ ሚዛን ላይ ይገኛል ብለን ምንወስደላቸው ብቸኛዋ ሰው ናቸው፡፡እንደሌላው የኮሚቴው አባል ሚሊዬነር ቢሆንም የሀብታቸው ምንጭ ከሀጥያት መንደር ያልተሰበሰበ ከክፋት ባህር ያልተጨለፈ ነው፡፡ ..አላቸው የሚባለውን ገንዘብም ከስግብግብነት በፀዳ መልኩ በአግባቡ የሚጠቀሙበት በስራዎቻቸው ያሉ በድርጅታቻቸው ተቀጥረው ለሚሰሩ ሰራተኛቻቸው ተገቢውን ክብር ሰጥተው ተገቢውን ክፍያ የሚከፍሉ..እንደወዳጅ የሚያዩ እንደእናት የሚንከባከቡ የመልካም ስነምግባር ባለቤት የሆኑ ክርስቲያ ናቸው፡፡
ሌላው አቶ ገመዳ ነገኦ ናቸው እሳቸው ደግሞ የሚገርመው የኤልያስ አባት ናቸው፡፡ኤልያስ ሌባው…ኤልያስ የኩማንደር መሀሪ የሚስጥራዊ ሸሪክ..ታዲያ ይሄ ለበጐ ስራ ታስቦ የተቋቋመው ኮሚቴ አባላት ውስጥ ሶስቱ ከኩማድር ጋር የተነካካ ነገር አላቸው..አራተኛው አባ ሽፍንፍንም ጐረቤቱ ናቸው… ለዛውም አንድ ህንጻ ተጋርተው የሚኖሩ ጐረቤታሞች፡፡ታዲያ ይሄ ኮሚቴ ከያዛቸው አባላት አንጻር አባላቱ ደግሞ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከኩማደር መሀሪያ ተፈላጊ ከመሆናቸው አንጻር ችግር ይፈጠር ይሆን…?፡፡
እዚህ ላይ አንድ መገለጽ ያለበት ጉዳይ አለ ኩማደር መሀሪ እና አባ ሽፍንፍን እዚህ ሻሸመኔ መኖር ከጀመሩ እንዲሁም አንድ ህንጻ ተጋርተው መኖር ከጀመሩ ስድስት ወራቶችን ያስቆጠሩ ቢሆንም በወሬ እና በዝና ካልሆነ በስተቀር አይተዋወቁም፡፡ አንደኛው አንደኛውን በአካል አይትቶ አያውቅም፡፡እርግጥ አባ ሽፍንፍን ከቤታቸው የሚወጡት በሳምንት አንድ ቀን ወይም ሁለት ቀን ብቻ ነው፡፡የሚከውኑትን ነገር የሚከውኑት …መሄድ የሚፈልጉበት ቦታ ሁሉ የሚሄዱት..ማድረግ የሚገባቸውን ነገር ሁሉ የሚያደርጉት በዛ ቀን ነው..የተቀረውን ቀን እቤታቸው ከቤታቸውም
‹የጽሞና መቅደስ›ብለው በሰየሙት የጸሎት ክፍላቸው ውስጥ ነው ተከርችመው የሚያሳልፉት ፡፡እንዲያም ሆኖ ታዲያ የውጩን ብርሀን በሚያዩበት እና ከህብረተሰቡ ጋር በሚቀላቀሉበት በእነዛ ውስን ቀናቶች በቅርብም በሩቅም የሚገኙ ብዛት ያላቸው የሻሸመኔ ኑዋሪዎች ሲያገኞቸው.. ሲተዋወቋቸው..አፍንጫቸው ስር ያለው ኩማደር ግን አይቻቸው አላውቅም ማለቱ የሚደንቅና ለሰሚው ግራ የሚያጋባ ታሪክ ነው።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
‹‹ይህ በጣም ጥሩ እና ከቅድስ ሰው የመነጨ ቅድስ ሀሳብ ነው፡፡ሁሉም የሻሸመኔ ምዕመን ባለው አቅም ይህን ዕቅዶትን ወደ ተግባር ለመቀየር እጁን ከመዘርጋ ወደ ኃላ አይልም..›› ብለው ንግግራቸውን በአጭር አጠናቀው፡ምዕመኑ በዕልልታ ደገፋቸው፡፡ተናጋሪውም ወደ መቀመጫቸው ተመለሱ፡፡
አሁንም ሌሎች ብዙ እጆች ተቀስረው ይታያሉ፡፡ብዙዎቹ የመናገር እድል ተሰጣቸው ሁሉም አቀራረብ ይለያይ እንጂ ተመሳሳይ የድጋፍ እና የአድናቆት ንግግራቸውን ነው ያሰሙት፡፡ከዛ ወደ ኮሚቴ መረጣው ተካሄደ በዚህ ኮሚቴ ውስጥ የተካከተቱት አምሰት ግለሳቦች ሲሆኑ ከአባ ሽፍንፍን በስተቀር ሁሉም በከተማዋ ዲታ የሚባሉ ግለሰቦች ናቸው፡፡አቶ ዳዊት ይግዛው..ወይዘሮ አረገዱ ይመር..አቶ ገመዳ ነገኦ እቶ ወርቅ አለማው እና አባ ሽፍንፍን ናቸው ፡፡
እስቲ ስለእነዚህ ኮሚቴዎች ዘርዘር ያለ ነገር እናውራ፡፡አምስቱም የተከበሩ የከተማዋ ሚሊዬነሮች ናቸው ብለን ተነጋግረናል፡፡ካሰቡበት እና ‹ከልብ ካለቀሱ እንባ አይገድም እንደሚባለው› ከምዕመኑ ሽራፊ ሳበራ ሳንቲም ሳይቀበሉ በቂ የሚባል ገንዘብ ማዋጣት እና የአባ ሽፍንፍንን ፕሮጀክት ወደ ተግባር የመቀየር ብቃትም አቅምም አላቸው፡፡
አቶ ዳዊት ይግዛው በከተማዋ ውስጥ ሁለት ትላልቅ ፋርማሲዎች ያሏቸው ሲሆን ዋና ስራቸው ግን በድብቅ በኬኒያ በኩል በህወጥ መንገድ የተለያዩ መድሀኒቶችን በማስገባት ለጠቅላላ ደቡባዊ የሀገሪቱ ክፍሎች እጥፍ በሆነ ትርፍ ማከፋፈል ነው፡፡ያም ነው ሚሊዬነር ያደረጋቸው፡፡እኚ ሰውዬ የአቶ ወርቅ አለማው የቅርብ ጓደኛ ናቸው..አብዛኛውን ስራዎቻቸውን አብረው ነው የሚሰሩት ፡፡
ወርቅ አለማው ማለት ደግሞ ማን እንደሆነ ሁላችሁም ታውቁታላችሁ፡፡ የኩማደር መሀሪ የቀድሞ እንጀራ አባት ነው፡፡በተጨማሪም የዚህ ኮሚቴም አንዱ አባል ነው፡፡
ሌላዋ የኮሚቴ አባል ወይዘሮ አረገዱ ናቸው..ምን አልባት እዚህ ኮሚቴ ውስጥ በሰውኛ ሚዛን ሲመዘኑ እዚህ ቤተክርስቲያን ቆመው ማምለካቸውና ማስቀደሳቸው ለይስሙላ እና ለታይታ አይደለም ምግባራቸውና እምነታቸው ተቀራራቢ ሚዛን ላይ ይገኛል ብለን ምንወስደላቸው ብቸኛዋ ሰው ናቸው፡፡እንደሌላው የኮሚቴው አባል ሚሊዬነር ቢሆንም የሀብታቸው ምንጭ ከሀጥያት መንደር ያልተሰበሰበ ከክፋት ባህር ያልተጨለፈ ነው፡፡ ..አላቸው የሚባለውን ገንዘብም ከስግብግብነት በፀዳ መልኩ በአግባቡ የሚጠቀሙበት በስራዎቻቸው ያሉ በድርጅታቻቸው ተቀጥረው ለሚሰሩ ሰራተኛቻቸው ተገቢውን ክብር ሰጥተው ተገቢውን ክፍያ የሚከፍሉ..እንደወዳጅ የሚያዩ እንደእናት የሚንከባከቡ የመልካም ስነምግባር ባለቤት የሆኑ ክርስቲያ ናቸው፡፡
ሌላው አቶ ገመዳ ነገኦ ናቸው እሳቸው ደግሞ የሚገርመው የኤልያስ አባት ናቸው፡፡ኤልያስ ሌባው…ኤልያስ የኩማንደር መሀሪ የሚስጥራዊ ሸሪክ..ታዲያ ይሄ ለበጐ ስራ ታስቦ የተቋቋመው ኮሚቴ አባላት ውስጥ ሶስቱ ከኩማድር ጋር የተነካካ ነገር አላቸው..አራተኛው አባ ሽፍንፍንም ጐረቤቱ ናቸው… ለዛውም አንድ ህንጻ ተጋርተው የሚኖሩ ጐረቤታሞች፡፡ታዲያ ይሄ ኮሚቴ ከያዛቸው አባላት አንጻር አባላቱ ደግሞ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከኩማደር መሀሪያ ተፈላጊ ከመሆናቸው አንጻር ችግር ይፈጠር ይሆን…?፡፡
እዚህ ላይ አንድ መገለጽ ያለበት ጉዳይ አለ ኩማደር መሀሪ እና አባ ሽፍንፍን እዚህ ሻሸመኔ መኖር ከጀመሩ እንዲሁም አንድ ህንጻ ተጋርተው መኖር ከጀመሩ ስድስት ወራቶችን ያስቆጠሩ ቢሆንም በወሬ እና በዝና ካልሆነ በስተቀር አይተዋወቁም፡፡ አንደኛው አንደኛውን በአካል አይትቶ አያውቅም፡፡እርግጥ አባ ሽፍንፍን ከቤታቸው የሚወጡት በሳምንት አንድ ቀን ወይም ሁለት ቀን ብቻ ነው፡፡የሚከውኑትን ነገር የሚከውኑት …መሄድ የሚፈልጉበት ቦታ ሁሉ የሚሄዱት..ማድረግ የሚገባቸውን ነገር ሁሉ የሚያደርጉት በዛ ቀን ነው..የተቀረውን ቀን እቤታቸው ከቤታቸውም
‹የጽሞና መቅደስ›ብለው በሰየሙት የጸሎት ክፍላቸው ውስጥ ነው ተከርችመው የሚያሳልፉት ፡፡እንዲያም ሆኖ ታዲያ የውጩን ብርሀን በሚያዩበት እና ከህብረተሰቡ ጋር በሚቀላቀሉበት በእነዛ ውስን ቀናቶች በቅርብም በሩቅም የሚገኙ ብዛት ያላቸው የሻሸመኔ ኑዋሪዎች ሲያገኞቸው.. ሲተዋወቋቸው..አፍንጫቸው ስር ያለው ኩማደር ግን አይቻቸው አላውቅም ማለቱ የሚደንቅና ለሰሚው ግራ የሚያጋባ ታሪክ ነው።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍2
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
:
✍ድርሰት:-በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ሄለን እና እናቷ ዲላ ከተማን ለቀው ሻሸመኔ አባ ሽፍንፍን ቤት ከከተሙ አንድ ወር አለፋቸው፡፡በነዚህ ቀናቷች ውስጥ በአባ ሽፍንፍን በሚደረግላቸው እንክብካቤ ደስተኟች ሆነዋል፡፡በተለይ ሄለን ከሲኦላዊው ጨለማ ኑሮ ወደ ገነታዊው ምቾት ኑሮ እንደመሸጋገር ቆጥራው ባጋጠማት እድል ተመስጣበታለች፡፡አሁን የጀመረችው አዲሱ ህይወቷ በጣም ተመችቷቷል….አረ ከመመቸትም በላይ ነው…ትምህርቷንም እዚሁ ሻሸመኔ ጀምራለች…አባ ልክ እንደመጣች ለእሷም ሆነ ለእናቷ ከደርዘን የበለጡ ልብሷችን ነው የገዙላቸው፡፡መቼስ ከለበሱት ልብስ በስተቀር የተቀረው ልብሶቻቸውም ሆነ መላ ንብረታቸው በእሳቱ ወድሞል ..አባ ታዲያ ከተቃጠለው ቤታቸው ጋር የወደመውን ተስፋቸውን ብቻ ሳይሆን ወደአመድእነት የተቀየረውን ቁሳቁሳቸውንም ነው መልሰው እየተኩላቸው ያለው፡፡
በተቃራኒው ለሄለን ሁሉ ነገር የተመቻትና ትክክል የሆነ ይምሰላት እንጂ የእኚህ አባ ሽፍንፍን ሁኔታ በጣም ግራ እየጋባት ነው፡፡ሁለ ነገራቸው ሚስጥር ነው..በአንድ ጎናቸው ስታስባቸው ፍፅም አለምን ችላ ብለው ለነፍሳቸው ብቻ ያደሩ ጻድቅ እና መንፈሰዊ አድባር አድርጋ ትስላቸዋለች…ለድሆች አባት ናቸው ..ለተጠቁት እና ለተበደሉት ደራሽ ናቸው…የጸሎት ክፍላቸው ውስጥ ገብተው ከመሸጉ ያለውሃ እና ምግብ ሶስት እና አራት ቀን በፀሎት ያሳልፋሉ…እኚን የመሰሉት ተግባሮቻቸው እንደ ፍጹማዊ ጻድቅ እንድታስባቸው ያስገድዳታል….
ግን ደግሞ አንዳንዴ መልሳ ፍጹምነታቸው ላይ በአዕምሮዋ ጥያቄ ይጫርባታል፡፡አለማዊ ፌልሞችን አብረዋት ቁጭ ብለው ያያሉ…ሙዚቃ ስታዳምጥ አብረው ባይዘፍኑም አብረዋት ያዳምጣሉ… ያለምንም ተቃውሞ የሙዚቃ ፍቅሯን እንድታዳብር ጊታር ገዝተው ሸልመዋታል….እና እኚን የመሰሉ ሌላኛውን ገጽታቸውን ስትገመመግም ደግሞ ግራ ትጋባለች……..ባለ መንታ ባህሪ ይሆኑባታል፡፡
ሄለን አሁን ሳሎን ብቻዋን ቁጭ ብላ ፊልም እያየች ነው፡፡
‹‹ምነው አንድ ቀን እንኳን እዚህ ክፍል ቢያስገቡኝ…?››ስትል ተመኘች
አባ ቀይ ቀሚስ አድርገው ፊታቸውን በጥቁር ሻርፕ ጠምጥመው እንደተለመደው ጥቁር መነጽራቸውን ሰክተውበታል
ሄለን ከመቀመጫዋ ተነሳችና በፈካ ፊት ተቀበለቻው፡፡አባ ዘወትር ከጐኗ ባይለዩ ደስ ይላታል፡፡ግን ውድ ናቸው፡፡ከደቂቃዎች ባለፈ ለእሷ ጊዜ የላቸውም…ምንም እንኳን እንድም ነገር ሳያጐድሉባ በምቾት ቢያኖሯትም ይሄ ለእሷ ጊዜ ያለመስጠታቸው ጉዳይ አልፎ አልፎም ቢሆን ያበሳጫታል፡፡በዝግታ የሚራመዱት አባ አጠገቧ ሲደርሱ መስቀላቸውን ሊያሳልሞት ወደግንባሯ ሰደዱ እና ካሳላሞት ቡኃላ ከጎኗ ተቀመጡ፡፡እሷግን ተነሳችና ወደ ኩሽና አመራች፤ እጅ ውሃ አመጣችና አስታጠበቻቸው…ምግብ አቀረበች..አብረው እየተጐራረሱ በሉ፡፡ይሄ ለሄለን በሳምንት አንድ ቀን ወይም ሁለት ቀን የሚገኝ እድል ነው፡፡ሁለቱም እስኪጠግቡ ከተመገቡ ቡኃላ መአዱ ተነሳ… አባ በተቀመጡበት ቦታ ሳይንቀሳቀሱ ወሬ ጀመሩ
‹‹እናትሽን ዲላ ሄዱ ነው ያልሺኝ?››
‹‹አዎ አባ?›››
‹‹ይመጣሉ..ወይስ ያድራሉ?›››
‹‹ትመጣለች››
‹‹አይ ጥሩ …በይ እንግዲህ የጀመርሽውን ፊልም እይ..እኔም የሆነች ስብሰባ አለችብኝ ወደ እዛው ላምራ ›› ብለው ከመቀመጫቸው ተነሱ…
‹‹ሊሄዱ ነው?›› አለች ሄለን ቅሬታ በሚነበብበት ድምጸት
‹‹አዎ ምነው ችግር አለ እንዴ?›››እጃቸውን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርገው በፍቅር አይን አትኩረው እየተመለከቷት ጠየቋት
‹‹አይ ምንም ችግር የለም ብቻ…››
‹‹ሄለን ልትነግሪኝ የፈለግሽው ነገር እንዳለ ያስታውቅብሻል ..ግድ የለም ንገሪኝ››
‹‹..ይሄ ጓረቤታችን ያለውን ሰውዬ ያውቁታል..?›››
‹‹የቱን ?››ግርታ ባረበበበት ስሜት ጠየቋት
‹‹ከላይኛው ፎቅ ላይ የሚኖረውን..ፖሊሱን››
‹‹ያን ያህል እንኳን አላውቀውም ምነው ጠየቅሺኝ?›››አጨንቁረው እየተመለከቷት የምትናገረውን ነገር ማዳመጥ ጀመሩ
‹‹እኔ እንጃ አዲስ አልሆነብኝም… ከዚህ በፊት የማውቀው ይመስለኛል..በዛ ላይ ሁል ጊዜ በተለይ ጥዋት ጥዋት ግቢ ውስጥ ጸሀዬን እየሞቅኩ ዘፈን ስለማመድ ድንገት በረንዳው ላይ ቆሞ ቁልቅል ወደ ታች እያየ ሲያዳምጠኝ አይና አፍራለው..
‹‹እንዴ ምን ያሳፍርሻል..ቢያዳምጥሽ ምን ችግር አለው?›››
‹‹እሱማ ምንም ችግር የለውም..ብቻ ዛሬ ጥዋት እንደበፊቱ አዳምጦ ብቻ ዝም አላለኝም….አናገረኝ››
‹‹ስዘፍን ድምጼ በጣም ቆንጆ እንደሆነ ነገረኝ…እሱም ለሙዚቃ ልዩ ፍቅር እንዳለውና ፒያኖ
እንደሚጫወት ካስረዳኝ ቡኃላ ፍቃደኛ ከሆንኩ ሊያለማምደኝ እንደሚችል ነገረኝ››
‹‹ታዲያ ምን አልሽው?››
‹‹እኔማ አስቤበት ነግርሀለው አልኩት››ብላ በዝርዝር አስረዳቻቸው
እሳቸውም ለደቂቃዎች በቆሙበት ካሰለሰሉ ቡኃላ‹‹እና ታዲያ ጥሩ ሀሳብ እኮ ነው..ያስተምርሻ፡፡ እዚሁ ደጃፍሽ እንዲህ አይነት ወርቅ እድል አግኝተሸማ መግፋት የለብሽም››በማለት ስትጨነቅ የዋለችበት ሀሳብ አቃለሉላት፡፡
‹‹ግን ማን እንደሆነ አውቀዋል አይደል..?ፓሊሱ …ኩማንደር መሀሪ የሚሉት ሰውዬ እኮ ነው..››
‹‹ይሁን ግድ የለም….በይ ደህና ሁኚ ››ብለው ግንባሯን ስመዋት በቆመችበት ጥለዋት ወጥተው ሄዱ
ከእሷቸው አገኘዋለው ያለችውን የይለፍ ፍቃድ እንዲህ በቀላሉ ማግኘቶ በጣም ነው ያስደሰታት
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
በመዲናዋ አዲስ አበባ ሳሪስ የተከፈተው ሮዝ ሆቴል በአጭር ጊዜ ውስጥ ታዋቂነትን አግኝቷል፤ገባያው ደርቷል..አብዛኛዎቹ ደንበኞቾ ዲታዎች የሚባሉ አይነቶች ናቸው፡፡ሁሉም የሮዝን ዝና ሰምተው ነው የተሰበሰቡት
‹‹አዲስ አበባ ከገባው የወሲብ ጥሜን የሚቆርጥልኝ..ረሀቤን የሚያራካልኝ ጀግና ወንድ እስከአሁን አልገጠመኝም….እዚህች ከተማ ውስጥ ወ ..ብቻ እንጂ ወንድ የለም ››ብላ አውጃለች ተብሎ ይወራባታል..አንድ ለአንዱ እያወራ እሲኪ ይህቺን ፎካሪ እንያት እየተባባሉ ይመጣሉ… በውበቷም በሳቋም ደንዝዘው እዛው ይቀራሉ..የእሷው ቤት አጫፋሪ …የእሷው ቤት አሞቂ እየሆኑ ይቀራሉ ..ከመካከላቸው ውስን የሆኑት ረጂም ምላስ ያለቸው እና ከእሽጋቸው ያልተፈቱ ብዙ እረብጣ ብሮችን ወርወር ማድረግ የሚችሉ ቱጃሮች ገላዋንም የመዳበስ ጭኖን ፈልቅቀው የመሞቅ ፍቃድ ያገኛሉ..ቀሪዎቹ ምራቃቸውን እንዳዝረከረኩ ይቀራሉ ….
አቤል ግን ደጋግሞ ሚያገኛት ..ደጋግሞ ሚያቅፋት..ደጋግሞ ሚያስተዳድራት ለስሜቷ ቅርብ የሆነ ብቸኛው ሰው መሆን ችሏል….ከንፈሯን እንዲስማት ምትፈቅድለት …እሷም የምትስመው ወዳጅ….‹ሮዝ ከማያውቁት ሰው ጋር ወይም ከማይወዱት ሰው ጋር ወሲብ መፈፀም ደስ ባያሰኝም ቀላል ነው…የልፈቀዱትን ሰው ከንፈር መምጠጥ ግን ያቅለሸልሻል››የሚል እምነት አለት፡፡
የሚገርመው አቤል ከሮዝ ጋር ባለው ግንኙነት በእሷ መንገድ እና ፕሮግራም ነው እየተጓዘ ያለው፡፡፡የምታደርጋቸውን ድርጊቷች በአጠቃላይ ያውቃቸዋል…ከሌሎች ወንዶች ጋር ምትከውነውን መዋደቅም በዝርዝር ይከታተላል ..ግን አንድም ቀን ከእሷ ጋር አንባ-ጓሮ ለመፍጠር ሞክሮ…ወይንም ማድረግ የፈለገችውን ነገር እንዳታደርግ ለማሰናካከል ሙከራ አድርጐ በፍጽም አያውቅም..ብቻ የእየ እለት እንቅስቃሴዋን በግልጽም በሚስጥርም እየተከታተላት በማስታወሻው ላይከመከተብ ተዘናግቶ አያውቅም፡፡
ዛሬ ካለውትሮዋ በጊዜ እቤቷ ገብታ ጥቅልል ብላ ተኝታለች፡፡የሆነ ውስጧ በማታውቀው ነገር እርብሽብሽ እያለባት ነው፡፡እንዲሁ ስትጨነቅ ነው የዋለችው..እርግጥ ይሄ ስሜት ከተጻናወታት ሰነባብቷል ..ሳምንታቶች አልፈዋል….ሀይለኛ የመደበት ስሜት
:
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
:
✍ድርሰት:-በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ሄለን እና እናቷ ዲላ ከተማን ለቀው ሻሸመኔ አባ ሽፍንፍን ቤት ከከተሙ አንድ ወር አለፋቸው፡፡በነዚህ ቀናቷች ውስጥ በአባ ሽፍንፍን በሚደረግላቸው እንክብካቤ ደስተኟች ሆነዋል፡፡በተለይ ሄለን ከሲኦላዊው ጨለማ ኑሮ ወደ ገነታዊው ምቾት ኑሮ እንደመሸጋገር ቆጥራው ባጋጠማት እድል ተመስጣበታለች፡፡አሁን የጀመረችው አዲሱ ህይወቷ በጣም ተመችቷቷል….አረ ከመመቸትም በላይ ነው…ትምህርቷንም እዚሁ ሻሸመኔ ጀምራለች…አባ ልክ እንደመጣች ለእሷም ሆነ ለእናቷ ከደርዘን የበለጡ ልብሷችን ነው የገዙላቸው፡፡መቼስ ከለበሱት ልብስ በስተቀር የተቀረው ልብሶቻቸውም ሆነ መላ ንብረታቸው በእሳቱ ወድሞል ..አባ ታዲያ ከተቃጠለው ቤታቸው ጋር የወደመውን ተስፋቸውን ብቻ ሳይሆን ወደአመድእነት የተቀየረውን ቁሳቁሳቸውንም ነው መልሰው እየተኩላቸው ያለው፡፡
በተቃራኒው ለሄለን ሁሉ ነገር የተመቻትና ትክክል የሆነ ይምሰላት እንጂ የእኚህ አባ ሽፍንፍን ሁኔታ በጣም ግራ እየጋባት ነው፡፡ሁለ ነገራቸው ሚስጥር ነው..በአንድ ጎናቸው ስታስባቸው ፍፅም አለምን ችላ ብለው ለነፍሳቸው ብቻ ያደሩ ጻድቅ እና መንፈሰዊ አድባር አድርጋ ትስላቸዋለች…ለድሆች አባት ናቸው ..ለተጠቁት እና ለተበደሉት ደራሽ ናቸው…የጸሎት ክፍላቸው ውስጥ ገብተው ከመሸጉ ያለውሃ እና ምግብ ሶስት እና አራት ቀን በፀሎት ያሳልፋሉ…እኚን የመሰሉት ተግባሮቻቸው እንደ ፍጹማዊ ጻድቅ እንድታስባቸው ያስገድዳታል….
ግን ደግሞ አንዳንዴ መልሳ ፍጹምነታቸው ላይ በአዕምሮዋ ጥያቄ ይጫርባታል፡፡አለማዊ ፌልሞችን አብረዋት ቁጭ ብለው ያያሉ…ሙዚቃ ስታዳምጥ አብረው ባይዘፍኑም አብረዋት ያዳምጣሉ… ያለምንም ተቃውሞ የሙዚቃ ፍቅሯን እንድታዳብር ጊታር ገዝተው ሸልመዋታል….እና እኚን የመሰሉ ሌላኛውን ገጽታቸውን ስትገመመግም ደግሞ ግራ ትጋባለች……..ባለ መንታ ባህሪ ይሆኑባታል፡፡
ሄለን አሁን ሳሎን ብቻዋን ቁጭ ብላ ፊልም እያየች ነው፡፡
‹‹ምነው አንድ ቀን እንኳን እዚህ ክፍል ቢያስገቡኝ…?››ስትል ተመኘች
አባ ቀይ ቀሚስ አድርገው ፊታቸውን በጥቁር ሻርፕ ጠምጥመው እንደተለመደው ጥቁር መነጽራቸውን ሰክተውበታል
ሄለን ከመቀመጫዋ ተነሳችና በፈካ ፊት ተቀበለቻው፡፡አባ ዘወትር ከጐኗ ባይለዩ ደስ ይላታል፡፡ግን ውድ ናቸው፡፡ከደቂቃዎች ባለፈ ለእሷ ጊዜ የላቸውም…ምንም እንኳን እንድም ነገር ሳያጐድሉባ በምቾት ቢያኖሯትም ይሄ ለእሷ ጊዜ ያለመስጠታቸው ጉዳይ አልፎ አልፎም ቢሆን ያበሳጫታል፡፡በዝግታ የሚራመዱት አባ አጠገቧ ሲደርሱ መስቀላቸውን ሊያሳልሞት ወደግንባሯ ሰደዱ እና ካሳላሞት ቡኃላ ከጎኗ ተቀመጡ፡፡እሷግን ተነሳችና ወደ ኩሽና አመራች፤ እጅ ውሃ አመጣችና አስታጠበቻቸው…ምግብ አቀረበች..አብረው እየተጐራረሱ በሉ፡፡ይሄ ለሄለን በሳምንት አንድ ቀን ወይም ሁለት ቀን የሚገኝ እድል ነው፡፡ሁለቱም እስኪጠግቡ ከተመገቡ ቡኃላ መአዱ ተነሳ… አባ በተቀመጡበት ቦታ ሳይንቀሳቀሱ ወሬ ጀመሩ
‹‹እናትሽን ዲላ ሄዱ ነው ያልሺኝ?››
‹‹አዎ አባ?›››
‹‹ይመጣሉ..ወይስ ያድራሉ?›››
‹‹ትመጣለች››
‹‹አይ ጥሩ …በይ እንግዲህ የጀመርሽውን ፊልም እይ..እኔም የሆነች ስብሰባ አለችብኝ ወደ እዛው ላምራ ›› ብለው ከመቀመጫቸው ተነሱ…
‹‹ሊሄዱ ነው?›› አለች ሄለን ቅሬታ በሚነበብበት ድምጸት
‹‹አዎ ምነው ችግር አለ እንዴ?›››እጃቸውን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርገው በፍቅር አይን አትኩረው እየተመለከቷት ጠየቋት
‹‹አይ ምንም ችግር የለም ብቻ…››
‹‹ሄለን ልትነግሪኝ የፈለግሽው ነገር እንዳለ ያስታውቅብሻል ..ግድ የለም ንገሪኝ››
‹‹..ይሄ ጓረቤታችን ያለውን ሰውዬ ያውቁታል..?›››
‹‹የቱን ?››ግርታ ባረበበበት ስሜት ጠየቋት
‹‹ከላይኛው ፎቅ ላይ የሚኖረውን..ፖሊሱን››
‹‹ያን ያህል እንኳን አላውቀውም ምነው ጠየቅሺኝ?›››አጨንቁረው እየተመለከቷት የምትናገረውን ነገር ማዳመጥ ጀመሩ
‹‹እኔ እንጃ አዲስ አልሆነብኝም… ከዚህ በፊት የማውቀው ይመስለኛል..በዛ ላይ ሁል ጊዜ በተለይ ጥዋት ጥዋት ግቢ ውስጥ ጸሀዬን እየሞቅኩ ዘፈን ስለማመድ ድንገት በረንዳው ላይ ቆሞ ቁልቅል ወደ ታች እያየ ሲያዳምጠኝ አይና አፍራለው..
‹‹እንዴ ምን ያሳፍርሻል..ቢያዳምጥሽ ምን ችግር አለው?›››
‹‹እሱማ ምንም ችግር የለውም..ብቻ ዛሬ ጥዋት እንደበፊቱ አዳምጦ ብቻ ዝም አላለኝም….አናገረኝ››
‹‹ስዘፍን ድምጼ በጣም ቆንጆ እንደሆነ ነገረኝ…እሱም ለሙዚቃ ልዩ ፍቅር እንዳለውና ፒያኖ
እንደሚጫወት ካስረዳኝ ቡኃላ ፍቃደኛ ከሆንኩ ሊያለማምደኝ እንደሚችል ነገረኝ››
‹‹ታዲያ ምን አልሽው?››
‹‹እኔማ አስቤበት ነግርሀለው አልኩት››ብላ በዝርዝር አስረዳቻቸው
እሳቸውም ለደቂቃዎች በቆሙበት ካሰለሰሉ ቡኃላ‹‹እና ታዲያ ጥሩ ሀሳብ እኮ ነው..ያስተምርሻ፡፡ እዚሁ ደጃፍሽ እንዲህ አይነት ወርቅ እድል አግኝተሸማ መግፋት የለብሽም››በማለት ስትጨነቅ የዋለችበት ሀሳብ አቃለሉላት፡፡
‹‹ግን ማን እንደሆነ አውቀዋል አይደል..?ፓሊሱ …ኩማንደር መሀሪ የሚሉት ሰውዬ እኮ ነው..››
‹‹ይሁን ግድ የለም….በይ ደህና ሁኚ ››ብለው ግንባሯን ስመዋት በቆመችበት ጥለዋት ወጥተው ሄዱ
ከእሷቸው አገኘዋለው ያለችውን የይለፍ ፍቃድ እንዲህ በቀላሉ ማግኘቶ በጣም ነው ያስደሰታት
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
በመዲናዋ አዲስ አበባ ሳሪስ የተከፈተው ሮዝ ሆቴል በአጭር ጊዜ ውስጥ ታዋቂነትን አግኝቷል፤ገባያው ደርቷል..አብዛኛዎቹ ደንበኞቾ ዲታዎች የሚባሉ አይነቶች ናቸው፡፡ሁሉም የሮዝን ዝና ሰምተው ነው የተሰበሰቡት
‹‹አዲስ አበባ ከገባው የወሲብ ጥሜን የሚቆርጥልኝ..ረሀቤን የሚያራካልኝ ጀግና ወንድ እስከአሁን አልገጠመኝም….እዚህች ከተማ ውስጥ ወ ..ብቻ እንጂ ወንድ የለም ››ብላ አውጃለች ተብሎ ይወራባታል..አንድ ለአንዱ እያወራ እሲኪ ይህቺን ፎካሪ እንያት እየተባባሉ ይመጣሉ… በውበቷም በሳቋም ደንዝዘው እዛው ይቀራሉ..የእሷው ቤት አጫፋሪ …የእሷው ቤት አሞቂ እየሆኑ ይቀራሉ ..ከመካከላቸው ውስን የሆኑት ረጂም ምላስ ያለቸው እና ከእሽጋቸው ያልተፈቱ ብዙ እረብጣ ብሮችን ወርወር ማድረግ የሚችሉ ቱጃሮች ገላዋንም የመዳበስ ጭኖን ፈልቅቀው የመሞቅ ፍቃድ ያገኛሉ..ቀሪዎቹ ምራቃቸውን እንዳዝረከረኩ ይቀራሉ ….
አቤል ግን ደጋግሞ ሚያገኛት ..ደጋግሞ ሚያቅፋት..ደጋግሞ ሚያስተዳድራት ለስሜቷ ቅርብ የሆነ ብቸኛው ሰው መሆን ችሏል….ከንፈሯን እንዲስማት ምትፈቅድለት …እሷም የምትስመው ወዳጅ….‹ሮዝ ከማያውቁት ሰው ጋር ወይም ከማይወዱት ሰው ጋር ወሲብ መፈፀም ደስ ባያሰኝም ቀላል ነው…የልፈቀዱትን ሰው ከንፈር መምጠጥ ግን ያቅለሸልሻል››የሚል እምነት አለት፡፡
የሚገርመው አቤል ከሮዝ ጋር ባለው ግንኙነት በእሷ መንገድ እና ፕሮግራም ነው እየተጓዘ ያለው፡፡፡የምታደርጋቸውን ድርጊቷች በአጠቃላይ ያውቃቸዋል…ከሌሎች ወንዶች ጋር ምትከውነውን መዋደቅም በዝርዝር ይከታተላል ..ግን አንድም ቀን ከእሷ ጋር አንባ-ጓሮ ለመፍጠር ሞክሮ…ወይንም ማድረግ የፈለገችውን ነገር እንዳታደርግ ለማሰናካከል ሙከራ አድርጐ በፍጽም አያውቅም..ብቻ የእየ እለት እንቅስቃሴዋን በግልጽም በሚስጥርም እየተከታተላት በማስታወሻው ላይከመከተብ ተዘናግቶ አያውቅም፡፡
ዛሬ ካለውትሮዋ በጊዜ እቤቷ ገብታ ጥቅልል ብላ ተኝታለች፡፡የሆነ ውስጧ በማታውቀው ነገር እርብሽብሽ እያለባት ነው፡፡እንዲሁ ስትጨነቅ ነው የዋለችው..እርግጥ ይሄ ስሜት ከተጻናወታት ሰነባብቷል ..ሳምንታቶች አልፈዋል….ሀይለኛ የመደበት ስሜት
❤2👍1
መንፈሶን እያናወጸው ነው፡፡ሚገርመው ለዚህ ስሜት መከሰት ምንም መነሻ ምክንያት የላትም ..ግን እንዲሁ ሁሉ ነገር አስጠልቷታል..መኖር እራሱ ይደክማት ጀምሯል፡፡‹‹ሰው..እንዴት ከለምንም መነሻ እንዲህ እርብሽብሽ ይላል››እራሷን በራሷ ስትጠይቃቸው የነበሩ ጥያቄዎች ናቸው፡፡በተኛችበት ከሁለት ሰዓት በላይ ብትገለባበጥም እንቅልፍ ሚባል ነገር ሊሞክራት አልቻለም..ያለፈው ምስቅልቅል ህይወቷ ቁርጥራጭ ትዝታዎች ከዚህም ከዚያም እየተበጣጠቁ ይመጡባታል…የልጅነት ህይወቷ…በደረቷ አጐጠጐጤ ስታወጣ የነበራት ደስታ…….ዲላን ለቃ አዲስአበባ አጐቷ ጋር ለመማር ስትመጣ እንዴት ፈንጥዛ እንደነበር..አጐቷ እንዴት ይንከባከባት እንደነበር…እሷም ምን ያህል በመንሰፍሰፍ አጐቷን ከአባትም በላይ ትወደው እንደነበር …...ብኃላ ህልሟን ሲያጨልመው የተሰማትን የጠቆረ ስሜት……በዛን ወቅት የገጠማትን የጸለመ ህይወት….ስለእርግዝናዋ…ወደ ዲላ ተመልሳ ገበና-ከታች በሆነችው እናቷ ጉያ ተሸሽጋ ስለመውለዷ…ከዛ ቡኃላ ስለተቀየረው ስብእናዋ….ስለአሳዘናቻቸው ወንዶች…ስለኩማንደር መሀሪ ምንም አልቀራትም……የሰላሳ አመት የህይወት ትዝታዋን በሁለት ሰዓት ውስጥ መልሳ ከለሰችው…..
እዛው ከትዝታዋ ሳትወጣ ነበር በራፏ የተንኳኳው፡፡እንደምንም ወደቀልቧ ተመለሰች እና ከተኛችበት ተነስታ ልትከፍት ሄደች….አቤል ነበር
ማንነቱን ስታውቅ በደስታ ተጠመጠመችበት እና በሞቀ ሳላምታ ተቀበለችው..በዚህ ድብርት በጠፈነጋት ሰዓት ብቸኛ ማግኘት እና ከጎኗ እንዲሆን የምትፈልገው ሰው ቢኖር አቤል ብቻ ነው…..ወደ ውስጥ ጐትታ አስገባችውና በራፉን መልሳ ቀርቅራ ከሳሎን ወደ መኝታ ቤት ይዛው ገባች..አልጋው ላይ ጎን ለጎን ተቀመጡ
‹‹ሆቴል መስለሺኝ እኮ እዛ ሔጄ ነበር…… እራሷን አሟት ወደ ቤት ሄዳለች አሉኝ ..ስልክሽም ጥሪ አይቀበልም፡፡ከዛ አላስችል ብሎኝ ሳላስፈቅድሽ መጣው….››
‹‹እንኳንም መጣህ… የእኔ የልብ አውቃ…በጣም ድብር ብሎኝ ነበር››
‹‹ምነው… ምን ሆንሺብኝ?››
‹‹ባክህ እርብሽብሽ ብዬለው..?››
ይሄ ስሜትሽ እኮ ሰነባበተብሽ ….ለመሆኑ ዛሬ ደግሞ ምን ገጠመሸ?››
‹‹አላውቅም… ምን አልባት ልጄ ሳትናፍቀኝ የቀረች አይመስለኝም…..››
‹‹ኦ ሄሊ እሷስ እኔንም ናፍቃኛለች..ከሳምንት ቡኃላ መልሼ ለመሄድ እቅድ አለኝ…እንደውም አሁን ለጉዞዬ የሚረዳኝን አንዳንድ ነገሮችን ላይ ብንነጋገር ደስ ይለኛል፡፡››
ሮዝ ልክ መስከረም ወር ላይ በየሜዳ ተራራው ፈክቶ እንደሚታ የአደይ አበባ ፊቷ በርቶ ‹‹የእውነት ፤ልትሄድ ነው…?››ስትል በአድናቆት ጠየቀችው
‹‹አዎ እሄዳለው… የጀመርኩትን ነገር እስካጠናቅቅ መመላለሴ የግድ ነው….እንቺ የእናትሽን ደረት ተንተርሰሽ ለልጅሸ ደግሞ በተራሽ እስክታንተራሺያት ድረስ እረፍት አይኖረኝም››
ሮዝ የተፍለቀለቀው ስሜቷ መልሶ በተስፋ መቁረጥ ጭልም አለ‹‹አይ…ይሳካል ብለህ ነው……?እኔ እንጃ ባክህ..ለማኛውም እስቲ በርታ››
‹‹እበረታለው….. ብቻ የአንቺም ትብብር ወሳኝነት አለው››አለት በሀዘኔታ እና ፍቅር መካከል በሚዋልል ስሜት በትኩረት እየተመለከታት
‹‹እኔ ምን ማድረግ እችላለው?››
‹‹የእሷን ጥያቄ ለመመለስ ሚያስችሉኝን ታሪኮችን ልትነግሪኝ እና ልትተባበሪልኝ ይገባል፡፡››
‹‹ምን አይነት ጥያቄ?››
‹‹አንዱ እና ወሳኙ አባቷ ማን እንደሆነ?››
ተንዘረዘረች‹‹ነገርኩህ እኮ …አባቷ ምን እንደሆነ አላ..ው…ቅ..ም››
‹‹የልጅሽን የተከረቸመ ልብ አለስልሶ ለመክፈት ወሳኙ ቁልፍ ግን ይሄን ጥያቄዋን መመለስ ብቻ ይመስለኛል ፡፡››
‹‹አልችልማ በቃ አላውቀውም አልኮችሁ እኮ!!!….ባውቀውም ልነግራት አልችልም..የእኔን ህመም ሚረዳልኝ እንዴት አንድ ሰው በዚህ አለም ላይ አጣለው…?እንዴት ህመሜን ብቻዬን ስታመም እኖራለው..?እንዴት የቁስሌ ጥዝጣዜ ሌላውን ሰው ሊሰማው አልቻለም..?ቢያንስ የመከራዬ መግል ሽታ እንዴት ነው የእኔ የሆኑትን ሰዎች እንኳን የማይሸታቸው..?››እየተንሰቀሰቀች መነፍረቅ ጀመረች…….ወደደረቱ ጎተተና አቀፎ ግባሯን በመሳም ቃላት ሳይጠቀም ፀጉሯን በማሻሸት ብቻ ያጽናናት ጀመረ
‹‹አቤልዬ›› ለስለስ ባለ ድምጽ ጠራችው
‹‹ወዬ እሮዝ››
‹‹በፈጠረህ አንድ ነገር ላስቸግርህ››
‹‹የፈለግሺውን››
‹‹ልጄ ጋ ደውልና እስኪ አውራት..ካንተጋ ስታወራ ቢያንስ ድምጾን ልስማው››
‹‹ምን ችግር አለው››ብሎ ሞባይሉን አወጣ እና ደወለ…ሞባይሉ ተነሳ
‹‹እንዴ !!አንተ አለህ እንዴ?ከዛኛው ጫፍ የመጣ ማራኪ የሄለን ድምጽ ነበር
‹‹ትክክለኛ ጥያቄ ነው……ባክሽ ከዛሬ ነገ በአካል እመጣለው ብዬ ሳስብ መደወሉን ተዘናጋው..ለመሆኑ ደህና ነሽ?››
‹‹ይመስገነው በጣም ሰላም ነኝ››
‹‹ማዘርሽስ?››
‹‹እኔ እያለውላት ምን ትሆናለች ብለህ ነው ለእሷ እኔ አለውላት…ለእኔ ደግሞ ፈጣሪ አለልኝ.. ስለዚህ ምንም አንሆን አትስጋ..››መለሰችለት
‹‹አሪፍ ገለጻ ነው..ይሄ ጣፋጭ ጫወታሽ በጣም ናፍቆኝ ነበር …እንግዲህ ተዘጋጂ የዛሬ ሳምንት አካባቢ እመጣለው››
‹‹የት?››
‹‹እንዴት….? የት… ?ዲላ ነዋ …ምነው ቀጠሮ እኮ አለን››
‹‹እሱማ አለን ግን…..››.
‹‹ግን ምን ?››
‹‹ዲላን እኮ ለቀናል››
ይሄንን ንግር ስትሰማ ሮዝ ከተቀመጠችበት አልጋ ላይ ተስፈንጥራ በመነሳት ቆመች..አቤልም ደነገጠ
‹‹ለቀናል ስትይ …አልገባኝም?››
‹‹ሻሸመኔ ገብተናል››
‹‹አሁንም አልገባኝም… በምን ምክንያት?››
‹‹አይ አንተ….በእኛ ቤት መጥተህ በሄድክ ማግስት ብዙ ተአምሮች ተከስተዋል..እንደውም ከዛሬ ነገ እያልኩ ተዘናጋው እንጂ ደውዬ ልነግርህ ሀሳቡ ነበረኝ..ባክህ ያልታሰቡ ሰዎች በለሊት እቤታችን ገብተው እኛን አውጥተው ሙሉ ቤታችንን …››በዚህ ጊዜ ላውድ የነበረውን ስልክ አጠፋውና ለብቻው ማደማጥ ጀመር ….ሮዝ እየተንቆራጠጠች ነው ..ከመጮኸ እራሷን ለመግታት እየታገለች ነው…
የሄለን ንግግር ቀጥሏል‹‹…ከእነ ሙሉ ዕቃው አንድደውት ሄዱ››
‹‹እነማን?››
‹‹ማነታቸውን ብናውቅማ ጥሩ ነበር…መቼስ እኔም ሆንኩ እማዬ በዚህ መጠን ሊበቀለን የሚችል ጠላት የለንም….. ምን አልባት የዛች የጓደኛህ ጣጣ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት አለኝ ..ደግሞም እርግጠኛ ነኝ ከዛ ውጭ አይሆንም››
‹‹እና ታዲያ አሁን ሻሸመኔ ማን ጋር ናችሁ?››
‹‹ሻሸመኔማ ያው ገነት ውስጥ ነን ብልህ ይቀላል …››ያሉበትን ቦታ ሁሉንም በዝርዝር አስረዳችው…ከመጣ ሻሸመኔ ድረስ መጥቶ ሊያገኛት እንደሚችል ነግራው ተሰናበተችው..ከዛ ቡኃላ የሮዝን ዓይን ማየት ነው የከበደው..የተሰበረ ልቧን በምን ቃላት ሊጠግንላት እንደሚችል ….ምን አይነት አይዞሽ ባይት ሊያጽናናት እንደሚችል ሊገለጽለት አልቻለም..ብቻ ዝም ብሎ ወደአልጋው ይዞት ወጣ..አንሶላውን ገለጠ እና ከስር እንድትገባ አደረጋት..ያለምንም መቃወም እንዳደረጋት ሆነችለት..እሱም ልብሱን አወለቀና ተከትሏት ከአንሶላው ውስጥ መሸገ…. ጭምቅ አድርጐ አቀፋት..በጣም ጭምቅ አድርጐ…ከገላው ጋር አጣብቆ…..
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
እዛው ከትዝታዋ ሳትወጣ ነበር በራፏ የተንኳኳው፡፡እንደምንም ወደቀልቧ ተመለሰች እና ከተኛችበት ተነስታ ልትከፍት ሄደች….አቤል ነበር
ማንነቱን ስታውቅ በደስታ ተጠመጠመችበት እና በሞቀ ሳላምታ ተቀበለችው..በዚህ ድብርት በጠፈነጋት ሰዓት ብቸኛ ማግኘት እና ከጎኗ እንዲሆን የምትፈልገው ሰው ቢኖር አቤል ብቻ ነው…..ወደ ውስጥ ጐትታ አስገባችውና በራፉን መልሳ ቀርቅራ ከሳሎን ወደ መኝታ ቤት ይዛው ገባች..አልጋው ላይ ጎን ለጎን ተቀመጡ
‹‹ሆቴል መስለሺኝ እኮ እዛ ሔጄ ነበር…… እራሷን አሟት ወደ ቤት ሄዳለች አሉኝ ..ስልክሽም ጥሪ አይቀበልም፡፡ከዛ አላስችል ብሎኝ ሳላስፈቅድሽ መጣው….››
‹‹እንኳንም መጣህ… የእኔ የልብ አውቃ…በጣም ድብር ብሎኝ ነበር››
‹‹ምነው… ምን ሆንሺብኝ?››
‹‹ባክህ እርብሽብሽ ብዬለው..?››
ይሄ ስሜትሽ እኮ ሰነባበተብሽ ….ለመሆኑ ዛሬ ደግሞ ምን ገጠመሸ?››
‹‹አላውቅም… ምን አልባት ልጄ ሳትናፍቀኝ የቀረች አይመስለኝም…..››
‹‹ኦ ሄሊ እሷስ እኔንም ናፍቃኛለች..ከሳምንት ቡኃላ መልሼ ለመሄድ እቅድ አለኝ…እንደውም አሁን ለጉዞዬ የሚረዳኝን አንዳንድ ነገሮችን ላይ ብንነጋገር ደስ ይለኛል፡፡››
ሮዝ ልክ መስከረም ወር ላይ በየሜዳ ተራራው ፈክቶ እንደሚታ የአደይ አበባ ፊቷ በርቶ ‹‹የእውነት ፤ልትሄድ ነው…?››ስትል በአድናቆት ጠየቀችው
‹‹አዎ እሄዳለው… የጀመርኩትን ነገር እስካጠናቅቅ መመላለሴ የግድ ነው….እንቺ የእናትሽን ደረት ተንተርሰሽ ለልጅሸ ደግሞ በተራሽ እስክታንተራሺያት ድረስ እረፍት አይኖረኝም››
ሮዝ የተፍለቀለቀው ስሜቷ መልሶ በተስፋ መቁረጥ ጭልም አለ‹‹አይ…ይሳካል ብለህ ነው……?እኔ እንጃ ባክህ..ለማኛውም እስቲ በርታ››
‹‹እበረታለው….. ብቻ የአንቺም ትብብር ወሳኝነት አለው››አለት በሀዘኔታ እና ፍቅር መካከል በሚዋልል ስሜት በትኩረት እየተመለከታት
‹‹እኔ ምን ማድረግ እችላለው?››
‹‹የእሷን ጥያቄ ለመመለስ ሚያስችሉኝን ታሪኮችን ልትነግሪኝ እና ልትተባበሪልኝ ይገባል፡፡››
‹‹ምን አይነት ጥያቄ?››
‹‹አንዱ እና ወሳኙ አባቷ ማን እንደሆነ?››
ተንዘረዘረች‹‹ነገርኩህ እኮ …አባቷ ምን እንደሆነ አላ..ው…ቅ..ም››
‹‹የልጅሽን የተከረቸመ ልብ አለስልሶ ለመክፈት ወሳኙ ቁልፍ ግን ይሄን ጥያቄዋን መመለስ ብቻ ይመስለኛል ፡፡››
‹‹አልችልማ በቃ አላውቀውም አልኮችሁ እኮ!!!….ባውቀውም ልነግራት አልችልም..የእኔን ህመም ሚረዳልኝ እንዴት አንድ ሰው በዚህ አለም ላይ አጣለው…?እንዴት ህመሜን ብቻዬን ስታመም እኖራለው..?እንዴት የቁስሌ ጥዝጣዜ ሌላውን ሰው ሊሰማው አልቻለም..?ቢያንስ የመከራዬ መግል ሽታ እንዴት ነው የእኔ የሆኑትን ሰዎች እንኳን የማይሸታቸው..?››እየተንሰቀሰቀች መነፍረቅ ጀመረች…….ወደደረቱ ጎተተና አቀፎ ግባሯን በመሳም ቃላት ሳይጠቀም ፀጉሯን በማሻሸት ብቻ ያጽናናት ጀመረ
‹‹አቤልዬ›› ለስለስ ባለ ድምጽ ጠራችው
‹‹ወዬ እሮዝ››
‹‹በፈጠረህ አንድ ነገር ላስቸግርህ››
‹‹የፈለግሺውን››
‹‹ልጄ ጋ ደውልና እስኪ አውራት..ካንተጋ ስታወራ ቢያንስ ድምጾን ልስማው››
‹‹ምን ችግር አለው››ብሎ ሞባይሉን አወጣ እና ደወለ…ሞባይሉ ተነሳ
‹‹እንዴ !!አንተ አለህ እንዴ?ከዛኛው ጫፍ የመጣ ማራኪ የሄለን ድምጽ ነበር
‹‹ትክክለኛ ጥያቄ ነው……ባክሽ ከዛሬ ነገ በአካል እመጣለው ብዬ ሳስብ መደወሉን ተዘናጋው..ለመሆኑ ደህና ነሽ?››
‹‹ይመስገነው በጣም ሰላም ነኝ››
‹‹ማዘርሽስ?››
‹‹እኔ እያለውላት ምን ትሆናለች ብለህ ነው ለእሷ እኔ አለውላት…ለእኔ ደግሞ ፈጣሪ አለልኝ.. ስለዚህ ምንም አንሆን አትስጋ..››መለሰችለት
‹‹አሪፍ ገለጻ ነው..ይሄ ጣፋጭ ጫወታሽ በጣም ናፍቆኝ ነበር …እንግዲህ ተዘጋጂ የዛሬ ሳምንት አካባቢ እመጣለው››
‹‹የት?››
‹‹እንዴት….? የት… ?ዲላ ነዋ …ምነው ቀጠሮ እኮ አለን››
‹‹እሱማ አለን ግን…..››.
‹‹ግን ምን ?››
‹‹ዲላን እኮ ለቀናል››
ይሄንን ንግር ስትሰማ ሮዝ ከተቀመጠችበት አልጋ ላይ ተስፈንጥራ በመነሳት ቆመች..አቤልም ደነገጠ
‹‹ለቀናል ስትይ …አልገባኝም?››
‹‹ሻሸመኔ ገብተናል››
‹‹አሁንም አልገባኝም… በምን ምክንያት?››
‹‹አይ አንተ….በእኛ ቤት መጥተህ በሄድክ ማግስት ብዙ ተአምሮች ተከስተዋል..እንደውም ከዛሬ ነገ እያልኩ ተዘናጋው እንጂ ደውዬ ልነግርህ ሀሳቡ ነበረኝ..ባክህ ያልታሰቡ ሰዎች በለሊት እቤታችን ገብተው እኛን አውጥተው ሙሉ ቤታችንን …››በዚህ ጊዜ ላውድ የነበረውን ስልክ አጠፋውና ለብቻው ማደማጥ ጀመር ….ሮዝ እየተንቆራጠጠች ነው ..ከመጮኸ እራሷን ለመግታት እየታገለች ነው…
የሄለን ንግግር ቀጥሏል‹‹…ከእነ ሙሉ ዕቃው አንድደውት ሄዱ››
‹‹እነማን?››
‹‹ማነታቸውን ብናውቅማ ጥሩ ነበር…መቼስ እኔም ሆንኩ እማዬ በዚህ መጠን ሊበቀለን የሚችል ጠላት የለንም….. ምን አልባት የዛች የጓደኛህ ጣጣ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት አለኝ ..ደግሞም እርግጠኛ ነኝ ከዛ ውጭ አይሆንም››
‹‹እና ታዲያ አሁን ሻሸመኔ ማን ጋር ናችሁ?››
‹‹ሻሸመኔማ ያው ገነት ውስጥ ነን ብልህ ይቀላል …››ያሉበትን ቦታ ሁሉንም በዝርዝር አስረዳችው…ከመጣ ሻሸመኔ ድረስ መጥቶ ሊያገኛት እንደሚችል ነግራው ተሰናበተችው..ከዛ ቡኃላ የሮዝን ዓይን ማየት ነው የከበደው..የተሰበረ ልቧን በምን ቃላት ሊጠግንላት እንደሚችል ….ምን አይነት አይዞሽ ባይት ሊያጽናናት እንደሚችል ሊገለጽለት አልቻለም..ብቻ ዝም ብሎ ወደአልጋው ይዞት ወጣ..አንሶላውን ገለጠ እና ከስር እንድትገባ አደረጋት..ያለምንም መቃወም እንዳደረጋት ሆነችለት..እሱም ልብሱን አወለቀና ተከትሏት ከአንሶላው ውስጥ መሸገ…. ጭምቅ አድርጐ አቀፋት..በጣም ጭምቅ አድርጐ…ከገላው ጋር አጣብቆ…..
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍6
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
:
✍ድርሰት:-በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ህይወት ወራጅ ወንዝ ነው-ክንውኑ ያስደምማል
ምንም ቋሚ ነገር የለም -ሁሉም ይጐርፋል…ይተማል
ተነባብሮ ተደራርቦ- ይፈናጠቃል ይፈሳል
በአጋጣሚ ያጣብቃል-ሳይታሰብ ያላቅቃል
ህይወት ወራጅ ወንዝ ነው -ድንገት ይጠባል… ይሰፋል
መዋኘት መፍሰስ የቻለን- ከአድማስ ባሻገር ያደርሳል
ተንፈራግጦ የታገለን -ከግንድ ያጋጫል ያጠፋል
ህይወት ወራጅ ወንዝ ነው- ነፍስ ይሰጣል…ነፍስ ይነጥቃል፡፡
--------------------------------------------------------------
‹‹ደከመሽ አይደል ?ብዙ ሰዓት እኮ ሰራን››አላት ከጐኗ ተነስቶ ፊት ለፊቷ በመቀመጥ
‹‹አረ አልደከመኝም አምስት ደቂቃም የቆየን አልመሰለኝም››በደስታ በተፍለቀለቀ እና በሚያበራ ፈገግታ መለሰችለት….
ኩማደር መሀሪ ለሄለን በገባላት ቃል መሰረት ፒያኖ ያሰለጥናት ከጀመረ ሳምንት አለፈው..በየቀኑ ከአንድ ሰዓት እስከ አንድ ሰዓት ተኩል… አንዳንዴም እስከ ሁለት ሰዓት በራሱ በተዘጋ የወንደላጤ ቤት ውስጥ ያሳልፍሉ..ሰዓቱ ደግሞ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ያለው ወደ ምሽቱ አካባቢ የተጠጋው ሰዓት ነው የመረጠጡት
ሄለን በመጀመሪያዎቹ ቀናት የኩማደርን ማንነት እና የት እንደምታውቀው ስለምታዉቅ ደንግጣ እና ግራ ተጋብታ ነበር…አዎ ዲላ ይኖር እንደነበረ እና ከሮዝ ጋር ግንኙነት እንደነበረው እሷንም ፍለጋ እቤት ድረስ መጥቶ በነበረበት ሰዓት አግኝታውዋለች በዚህም የተነሳ ያቀረበላትን ጥያቄ ለመቀበል እና ላለመቀበል ከራሷ ጋር ብዙ ተታግላ ነበር..ቡኃላ ግን እስኪ ልሞክረው ብላ ጀመረች..ዋል አደር ስትል ግን ጭራሽ ነገሩን እየዘነጋችው መጣች…አቀራረቡ …ለእሷ የሚያደርገው እንክብካቤ ልክ ተወዳጅ ታላቅ ወንድሞ መስሎ እንዲታያት ማድረግ ችሎል፡፡በአጠቃላይ ስሜቷን ተቆጣጥሯል ፡፡
…ኩማንደር መሀሪ ደግሞ እስከአሁን ብዙ ነገር እያነሳ ከእሷ ጋር ማውራት ቢችልም ስለዲላ ትንፍሽ ብሎላት አያውቅም…ስለእሷ ባሰበ ቁጥር ግራ ይጋባል..በጣም ታሳዝነዋለች…ከክፉ መሀፀን በቅላ….ክፉ እጅ ላይ ወደቀች…ምንም ማድረግ አይችልም..ይሄ በአለም ያለ ነባራዊ ሁኔታ እና በየእለቱ የሚከሰት ተግባር ነው..በዚህን አይነት ጊዜ ለሀጥአን መቀጣጫ ታስቦ የዘነበ መአት ጻድቃኖችን መለብለቡ አይቀርም…..
አብረው ፒያኖ ከመለማመድ ውጭ ስለእናቷ አውርተው አያውቁም ስለእሷ ብታወራ ጥሩ ስሜት እንደማይሰማው ታውቃለች ሄለን ብዙ ነገር ይቀርብኛል ብላም ታስባለች በጋራ እንኳን አቅድውት ስለነበረው ሄለን ስለአባቷ ጉዳይ በራሷ ድምፅ ቀድታ ለሷ እንዲያሰማት አቅደው ነበር ስለሱ እንኳን አንስታ ማውራት አልፈለገችም
ሙዚቃ መለማመዱ ብቻ አይደለም የሚቀርባት…ለአባትነት የቀረበው ወንድምነቱ ይቀርባታል..በጣም ለምዳዋለች…ሰው እንዴት በሳምንት እንዲህ ሰውን ይለምዳል..?ለራሷም እየገረማት ነው…
‹‹ትኩስ ሀይል አይደለሽ…መች በቀላሉ ትደክሚያለሽ››አላት
አልመለሰችለትም..እንደማፈር ብላ አንገቷን አቀረቀረች..
ለደቂቃዎች ዝም ተባባሉ…ዝም ሲል ተፈራዋለች….‹‹ምነው ዝም አልክ?››
‹‹ኦ ይቅርታ በሀሳብ እኮ ጭልጥ አልኩ..ስለአባ ሽፍንፍን እያሰብኩ ነበር››
‹‹ስለእሷቸው ምን የሚያሳስብ ጉዳይ አለ? ምነው የሚያሳስር ወንጀል አገኘህባቸው እንዴ?››
‹‹በፍጹም ….ፃድቅ ናቸው ይባሉ የለ እንዴ .. ?እንዴት ወንጃል ላገኝባቸው እችላለው..?ደግሞስ ወንጀል አገኘውባቸው ብልስ እንደ መላአክ የሚያያቸው የሻሸመኔ ኑዋሪ የሚያምነኝ ይመስልሻል…?ሰላማዊ ሰልፍ ነው የሚወጡብኝ፡፡ ››
‹‹እና ሌላ ስለእሷቸው ምን አሳሰበህ?››
‹‹ብዙ ብዙ ነገር ነዋ..ለመሆኑ አሁን ወደ እኔ ስትመጪ እቤት ነበሩ?››
‹‹አዎ …ትናንት ፀሎት ቤታቸው ገብተው እንደጠረቀሙ ናቸው››
‹‹ለዚህን ያህል ረጂም ጊዜ ይፀልያሉ ማለት ነው?››
‹‹ሁለት ቀን ምን አላት …?ሶስት እና አራት ቀን ነው የሚቆዩት ….እንዴት ሰው ለዚህ ሁሉ ቀን ያለምግብ እና መጠጥ ብቻውን ቤት ዘግተው ማሳለፍ ይችላል?ለእኔም በጣም የሚገርም ተአምር ነው፡፡በቃ የከተማ መናኝ በላቸው››
‹‹አንቺስ አብረሻቸው አትፀልይም?››
‹‹አረ በፍጹም …ወደ ጸሎት ክፍላቸው ሲያስገቡኝ አይደል?››ብላ አይኗን ወደ ኩማንደሩ አንድ የተዘጋ ክፍል ወረወረች…ይህቺ ክፍል ልክ እንደ አባ የፀሎት ክፍል ሁሌ በመጣች ቁጥር ተቆልፎ ነው የምታገኘው..ደግሞ ይህቺ ዝግ ክፍል እታች ምድር ላይ ከሚገኘው የአባ ፀሎት ቤት ጋር በትይዩ አቅጣጫ መገኘቱ ግርምት ይፈጥርባታል…
‹‹ጥሩ ነው…ግን አሁን አሁን እየወደድኮቸው መጥቼያለው መሰለኝ››
ከት ብላ ሳቀችና ‹‹እንዴ …በፊት ትጠላቸው ነበር እንዴ?››
‹‹እንደ እሱ ማለቴ እንኳን አይደለም…በፊት ስለእሷ
ስለእሳቸው ፍቅርም ሆነ ጥላቻ በውስጤ አልነበረም..አሁን ግን..››
‹‹እሺ አሁን እንዴት ልትወዳቸው ቻልክ?››
‹‹ባንቺ ምክንያት ነዋ..እሷ
እሳቸው ወደ እዚህ ባያመጡሽ ከእኔ ጋር አንገናኘም ነበር…››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው››አለችው እንደመተከዝ ብላ
‹‹ይገርምሻል ሄለን አንዳንዴ ሳስበው በውሳኔዬ ላይ ጥርጣሬ ያድርብኛል››
‹‹በየትኛው ውሳኔህ?››
‹‹አንቺን ፒያኖ ላሰልጥንሽ ብዬ መጀመሬን….››ብሩህ የነበረው የሄለን የፊት ገጽታ በአንዴ ጭላሼት ለበሰ
‹‹እሱ እንኳን ትክክል ነህ… እኔም በጣም እራስ ወዳድ እንደሆንኩ እየተሰማኝ ነው….. ጊዜህን በጣም እየተሸማውብህ ነው..››
‹‹ኖ..ኖ እንደእዛ ማለቴ አይደለም…ካንቺ ጋር ማሳልፋት እያንዳዶ ደቂቃ ለስጋዬም ሆነ ለመንፈሴ ምን ያህል መነቃቃት እና ደስታ እንደሚፈጥርብኝ መገመት አትቺይም…አነቺ እዚህ ቤት ስትገቢ እናቴ እንደመጣችነው መስሎ ነው ሚሰማኝ››
ድፍርስ ብሎ የነበረው ስሜቷ በሰኮንዶች ውስጥ መልሶ አንሰራራ‹‹እና ታዲያ ውሳኔህ ላይ እንዴት ጥርጣሬ ሊያድርብህ ቻለ?››
‹‹አየሽ..ፍቅር ያስፈራኛል…አባቴን እና እናቴን በሞት ከተነጠቅኩ ብኃላ ሌላ ሰው የእኔ ነው ብዬ መቅረብ እና መልመድ ፈራለው…ምክንያም ከመልመድ ውስጥ ፍቅር ተፈልፍሎ መውጣቱ አይቀርም….ያንን ፍቅር ደግሞ በሆነ አጋጣሚ መልሶ የማጣት ዕጣ ቢያጋጥመኝ ዳግም መቋቋም የምችል አይመስለኝም..በዚህ የተነሳ ከእናቴ ሞት ጀምሮ ላለፉት ሶስት አመታት ሰውን ስሸሽ እና በራሴ የብቸኝነት ዋሻ ውስጥ ስወሸቅ ነው የከረምኩት፤ አሁን ግን በዚህች አንድ ሳምንት ውስጥ በጣም እየለመድኩሽ መሆኑን ሳስብ እየፈራው ነው…ማታ ሸኝቼሽ በማግስቱ የመለማመጃ ሰዓታችን ደርሷ እስክትመጪ ጊዜው በጣም ይረዝምብኝ ጀምሯል….››በማለት ከእሱ አንደበት እሰማዋለው ብላ ያላሰበችውን ..የጉርምስና ልቧን በአንዴ የሚደረማምስ የማላውቀው አባቴ አንድ ቀን መጥቶ ይነግረኛል ብላ በተስፋ ትጠብቀው የነበረውን የሚያቀልጥ የፍቅር እና የመፈለግ ዜና የሚያበስሩ ቃላቶችን ለአንድ ሳምንት የተወዋወቀችው ይሄ ኩማደር አበሰራት..ውስጦ በደስታ እረሰረሰ..እንባዋም በአይኖቾ ከፍቃዷ ውጭ ተነኮለለ…
‹‹ኩማደር..ከዚህ በፊት ስለደረሰብህ ሀዘን እና ብቸኝነት በእውነት በጣም አዝናለው..ፍቅርን ማጣት ምን ማለት እንደሆነና በልብ ውስጥ ምን አይነት ሽንቁር እንደሚፈጥር በደንብ አውቃለው..እኔም ሙሉ የቤተሰብ ፍቅር አግኝቼ አይደለም እየኖርኩ ያለውት ..ግን አሁን ያልከው ፍቅርን የመፍራት አባዜህ እኔን ፒያኖ ከማሰልጠን ጋር ምን እንዳቆራኘው አሁንም አልገባኝም?››ጠየቀችው ይበልጥ ሚያመሞቅ ንግግር ከእሱ መስማት ፈልጋ…
‹‹አየሽ ሄለን ይሄ ፒያኖ ልምዳችን ለሶስት ወር ወይም ለአራት
:
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
:
✍ድርሰት:-በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ህይወት ወራጅ ወንዝ ነው-ክንውኑ ያስደምማል
ምንም ቋሚ ነገር የለም -ሁሉም ይጐርፋል…ይተማል
ተነባብሮ ተደራርቦ- ይፈናጠቃል ይፈሳል
በአጋጣሚ ያጣብቃል-ሳይታሰብ ያላቅቃል
ህይወት ወራጅ ወንዝ ነው -ድንገት ይጠባል… ይሰፋል
መዋኘት መፍሰስ የቻለን- ከአድማስ ባሻገር ያደርሳል
ተንፈራግጦ የታገለን -ከግንድ ያጋጫል ያጠፋል
ህይወት ወራጅ ወንዝ ነው- ነፍስ ይሰጣል…ነፍስ ይነጥቃል፡፡
--------------------------------------------------------------
‹‹ደከመሽ አይደል ?ብዙ ሰዓት እኮ ሰራን››አላት ከጐኗ ተነስቶ ፊት ለፊቷ በመቀመጥ
‹‹አረ አልደከመኝም አምስት ደቂቃም የቆየን አልመሰለኝም››በደስታ በተፍለቀለቀ እና በሚያበራ ፈገግታ መለሰችለት….
ኩማደር መሀሪ ለሄለን በገባላት ቃል መሰረት ፒያኖ ያሰለጥናት ከጀመረ ሳምንት አለፈው..በየቀኑ ከአንድ ሰዓት እስከ አንድ ሰዓት ተኩል… አንዳንዴም እስከ ሁለት ሰዓት በራሱ በተዘጋ የወንደላጤ ቤት ውስጥ ያሳልፍሉ..ሰዓቱ ደግሞ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ያለው ወደ ምሽቱ አካባቢ የተጠጋው ሰዓት ነው የመረጠጡት
ሄለን በመጀመሪያዎቹ ቀናት የኩማደርን ማንነት እና የት እንደምታውቀው ስለምታዉቅ ደንግጣ እና ግራ ተጋብታ ነበር…አዎ ዲላ ይኖር እንደነበረ እና ከሮዝ ጋር ግንኙነት እንደነበረው እሷንም ፍለጋ እቤት ድረስ መጥቶ በነበረበት ሰዓት አግኝታውዋለች በዚህም የተነሳ ያቀረበላትን ጥያቄ ለመቀበል እና ላለመቀበል ከራሷ ጋር ብዙ ተታግላ ነበር..ቡኃላ ግን እስኪ ልሞክረው ብላ ጀመረች..ዋል አደር ስትል ግን ጭራሽ ነገሩን እየዘነጋችው መጣች…አቀራረቡ …ለእሷ የሚያደርገው እንክብካቤ ልክ ተወዳጅ ታላቅ ወንድሞ መስሎ እንዲታያት ማድረግ ችሎል፡፡በአጠቃላይ ስሜቷን ተቆጣጥሯል ፡፡
…ኩማንደር መሀሪ ደግሞ እስከአሁን ብዙ ነገር እያነሳ ከእሷ ጋር ማውራት ቢችልም ስለዲላ ትንፍሽ ብሎላት አያውቅም…ስለእሷ ባሰበ ቁጥር ግራ ይጋባል..በጣም ታሳዝነዋለች…ከክፉ መሀፀን በቅላ….ክፉ እጅ ላይ ወደቀች…ምንም ማድረግ አይችልም..ይሄ በአለም ያለ ነባራዊ ሁኔታ እና በየእለቱ የሚከሰት ተግባር ነው..በዚህን አይነት ጊዜ ለሀጥአን መቀጣጫ ታስቦ የዘነበ መአት ጻድቃኖችን መለብለቡ አይቀርም…..
አብረው ፒያኖ ከመለማመድ ውጭ ስለእናቷ አውርተው አያውቁም ስለእሷ ብታወራ ጥሩ ስሜት እንደማይሰማው ታውቃለች ሄለን ብዙ ነገር ይቀርብኛል ብላም ታስባለች በጋራ እንኳን አቅድውት ስለነበረው ሄለን ስለአባቷ ጉዳይ በራሷ ድምፅ ቀድታ ለሷ እንዲያሰማት አቅደው ነበር ስለሱ እንኳን አንስታ ማውራት አልፈለገችም
ሙዚቃ መለማመዱ ብቻ አይደለም የሚቀርባት…ለአባትነት የቀረበው ወንድምነቱ ይቀርባታል..በጣም ለምዳዋለች…ሰው እንዴት በሳምንት እንዲህ ሰውን ይለምዳል..?ለራሷም እየገረማት ነው…
‹‹ትኩስ ሀይል አይደለሽ…መች በቀላሉ ትደክሚያለሽ››አላት
አልመለሰችለትም..እንደማፈር ብላ አንገቷን አቀረቀረች..
ለደቂቃዎች ዝም ተባባሉ…ዝም ሲል ተፈራዋለች….‹‹ምነው ዝም አልክ?››
‹‹ኦ ይቅርታ በሀሳብ እኮ ጭልጥ አልኩ..ስለአባ ሽፍንፍን እያሰብኩ ነበር››
‹‹ስለእሷቸው ምን የሚያሳስብ ጉዳይ አለ? ምነው የሚያሳስር ወንጀል አገኘህባቸው እንዴ?››
‹‹በፍጹም ….ፃድቅ ናቸው ይባሉ የለ እንዴ .. ?እንዴት ወንጃል ላገኝባቸው እችላለው..?ደግሞስ ወንጀል አገኘውባቸው ብልስ እንደ መላአክ የሚያያቸው የሻሸመኔ ኑዋሪ የሚያምነኝ ይመስልሻል…?ሰላማዊ ሰልፍ ነው የሚወጡብኝ፡፡ ››
‹‹እና ሌላ ስለእሷቸው ምን አሳሰበህ?››
‹‹ብዙ ብዙ ነገር ነዋ..ለመሆኑ አሁን ወደ እኔ ስትመጪ እቤት ነበሩ?››
‹‹አዎ …ትናንት ፀሎት ቤታቸው ገብተው እንደጠረቀሙ ናቸው››
‹‹ለዚህን ያህል ረጂም ጊዜ ይፀልያሉ ማለት ነው?››
‹‹ሁለት ቀን ምን አላት …?ሶስት እና አራት ቀን ነው የሚቆዩት ….እንዴት ሰው ለዚህ ሁሉ ቀን ያለምግብ እና መጠጥ ብቻውን ቤት ዘግተው ማሳለፍ ይችላል?ለእኔም በጣም የሚገርም ተአምር ነው፡፡በቃ የከተማ መናኝ በላቸው››
‹‹አንቺስ አብረሻቸው አትፀልይም?››
‹‹አረ በፍጹም …ወደ ጸሎት ክፍላቸው ሲያስገቡኝ አይደል?››ብላ አይኗን ወደ ኩማንደሩ አንድ የተዘጋ ክፍል ወረወረች…ይህቺ ክፍል ልክ እንደ አባ የፀሎት ክፍል ሁሌ በመጣች ቁጥር ተቆልፎ ነው የምታገኘው..ደግሞ ይህቺ ዝግ ክፍል እታች ምድር ላይ ከሚገኘው የአባ ፀሎት ቤት ጋር በትይዩ አቅጣጫ መገኘቱ ግርምት ይፈጥርባታል…
‹‹ጥሩ ነው…ግን አሁን አሁን እየወደድኮቸው መጥቼያለው መሰለኝ››
ከት ብላ ሳቀችና ‹‹እንዴ …በፊት ትጠላቸው ነበር እንዴ?››
‹‹እንደ እሱ ማለቴ እንኳን አይደለም…በፊት ስለእሷ
ስለእሳቸው ፍቅርም ሆነ ጥላቻ በውስጤ አልነበረም..አሁን ግን..››
‹‹እሺ አሁን እንዴት ልትወዳቸው ቻልክ?››
‹‹ባንቺ ምክንያት ነዋ..እሷ
እሳቸው ወደ እዚህ ባያመጡሽ ከእኔ ጋር አንገናኘም ነበር…››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው››አለችው እንደመተከዝ ብላ
‹‹ይገርምሻል ሄለን አንዳንዴ ሳስበው በውሳኔዬ ላይ ጥርጣሬ ያድርብኛል››
‹‹በየትኛው ውሳኔህ?››
‹‹አንቺን ፒያኖ ላሰልጥንሽ ብዬ መጀመሬን….››ብሩህ የነበረው የሄለን የፊት ገጽታ በአንዴ ጭላሼት ለበሰ
‹‹እሱ እንኳን ትክክል ነህ… እኔም በጣም እራስ ወዳድ እንደሆንኩ እየተሰማኝ ነው….. ጊዜህን በጣም እየተሸማውብህ ነው..››
‹‹ኖ..ኖ እንደእዛ ማለቴ አይደለም…ካንቺ ጋር ማሳልፋት እያንዳዶ ደቂቃ ለስጋዬም ሆነ ለመንፈሴ ምን ያህል መነቃቃት እና ደስታ እንደሚፈጥርብኝ መገመት አትቺይም…አነቺ እዚህ ቤት ስትገቢ እናቴ እንደመጣችነው መስሎ ነው ሚሰማኝ››
ድፍርስ ብሎ የነበረው ስሜቷ በሰኮንዶች ውስጥ መልሶ አንሰራራ‹‹እና ታዲያ ውሳኔህ ላይ እንዴት ጥርጣሬ ሊያድርብህ ቻለ?››
‹‹አየሽ..ፍቅር ያስፈራኛል…አባቴን እና እናቴን በሞት ከተነጠቅኩ ብኃላ ሌላ ሰው የእኔ ነው ብዬ መቅረብ እና መልመድ ፈራለው…ምክንያም ከመልመድ ውስጥ ፍቅር ተፈልፍሎ መውጣቱ አይቀርም….ያንን ፍቅር ደግሞ በሆነ አጋጣሚ መልሶ የማጣት ዕጣ ቢያጋጥመኝ ዳግም መቋቋም የምችል አይመስለኝም..በዚህ የተነሳ ከእናቴ ሞት ጀምሮ ላለፉት ሶስት አመታት ሰውን ስሸሽ እና በራሴ የብቸኝነት ዋሻ ውስጥ ስወሸቅ ነው የከረምኩት፤ አሁን ግን በዚህች አንድ ሳምንት ውስጥ በጣም እየለመድኩሽ መሆኑን ሳስብ እየፈራው ነው…ማታ ሸኝቼሽ በማግስቱ የመለማመጃ ሰዓታችን ደርሷ እስክትመጪ ጊዜው በጣም ይረዝምብኝ ጀምሯል….››በማለት ከእሱ አንደበት እሰማዋለው ብላ ያላሰበችውን ..የጉርምስና ልቧን በአንዴ የሚደረማምስ የማላውቀው አባቴ አንድ ቀን መጥቶ ይነግረኛል ብላ በተስፋ ትጠብቀው የነበረውን የሚያቀልጥ የፍቅር እና የመፈለግ ዜና የሚያበስሩ ቃላቶችን ለአንድ ሳምንት የተወዋወቀችው ይሄ ኩማደር አበሰራት..ውስጦ በደስታ እረሰረሰ..እንባዋም በአይኖቾ ከፍቃዷ ውጭ ተነኮለለ…
‹‹ኩማደር..ከዚህ በፊት ስለደረሰብህ ሀዘን እና ብቸኝነት በእውነት በጣም አዝናለው..ፍቅርን ማጣት ምን ማለት እንደሆነና በልብ ውስጥ ምን አይነት ሽንቁር እንደሚፈጥር በደንብ አውቃለው..እኔም ሙሉ የቤተሰብ ፍቅር አግኝቼ አይደለም እየኖርኩ ያለውት ..ግን አሁን ያልከው ፍቅርን የመፍራት አባዜህ እኔን ፒያኖ ከማሰልጠን ጋር ምን እንዳቆራኘው አሁንም አልገባኝም?››ጠየቀችው ይበልጥ ሚያመሞቅ ንግግር ከእሱ መስማት ፈልጋ…
‹‹አየሽ ሄለን ይሄ ፒያኖ ልምዳችን ለሶስት ወር ወይም ለአራት
👍1
ወር ቢቆይ ነው..ከዛ ቡኃላ በቃ ግንኙነታችን ይቋረጣል ማለት ነው…አየሽ ያ ማለት ደግሞ ለምጄ አጣውሽ ማለት አይደል… ?ይሄ የሰው ትንፋሽ የለመደው የወንደላጤ ቤቴ መልሶ ቀዘቀዘ ማለት አይደል..?››
‹‹አይደለም…. በፍፅም አይደለም….አኔ በእዚህ ትውውቃችን ምን ያህል ደስተኞች እንደሆንኩ አታውቅም ….እዚህ ቤትህ ስመጣ ለፒያኖ ለመለማመድ ብቻ እንዳይመስልህ…..ልክ ታላቅ ወንድሜ ቤት እንደምመጣ አይነት እየተሰማኝ ነው ምመጣው..መቼም ይሄንን ግንኙነታችንን ማቋረጥ አልፈልግም …ሁሌ ከስርህ የማትጠፋ ታናሽ እህትህ መሆን ነው የምፈልገው ….›› አለችው በፈገግታ
‹‹አመሰግናለው››አላት በእርካታ…አዎ አሁን ቀስ በቀስ የወጣትነት አማኝ ልቧን በመሸርሸር ወደ ሚፈልገው መስመር እያስገባት መሆኑን በመረዳቱ ለስኬታማነቱ እራሱን በውስጡ አደነቀ…..
‹‹እሺ ወንድም ጋሼ አሁን በጣም መሸ ልሂድ›› ብላ ከመቀመጫዋ ተነሳች….
‹‹አንቺ አሪፍ ስምነው ያወጣሺልኝ… ወንድም ጋሼ ነው ያልሺኝ?››እያለ ከመቀመጫው ተነሳ እና እጁን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርጎ ውጭ ድረስ ሸኛት ‹‹መልካም ለሊት… መልካም ህልም ››በማለት ወደ ራሱ ጐትቶ ግንባሯን ሳመና በቆመችበት ጥሎት ፊቱን አዙሮ ወደቤት ተመለሰ..
እሷም ልትገምታቸው ላልቻለቻቸው ሴኮንዶች ባለችበት ፈዛ ቆመች..የሆነ የማታውቀው ስሜት ነው የተሰማት ..ከዚህ በፊት እንዲህ ከሰውነቷ ልጥፍ ብሎባትም የሳማት ሰው መኖሩን አታስታውስም……. በጣም ያስገረማት ደገሞ በእሱ መሳሙ ሳይሆን መሳሙን ተከትሎ በውስጧ የተፈጠረባት ምንነቱን መለየት ያልቻለችው ግራ አጋቢ ስሜት ነው...ብዥ ነው ያለባት….እንዴት ከተገተረችበት ተንቀሳቅሳ ዞራ እቤቷ እንደደረሰች ራሱ አታውቅም
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ሮዝ እና አቤል ወደ ሻሸመኔ እየሄዱ ነው፡፡በህዝብ ትራንስፖር አይደለም የሚጓዙት….ሮዝ በተከራየችው የቤት መኪና በአቤል ሾፋሪነት ነው፡፡
ሮዝ በዚህ ሰዓት ወደ ሻሸመኔ የምትጓዘው ለመዝናንተ ወይም ለሽርሽር አይደለም…ተገዳ ነው…የምታደርገው ጠፍቷት ነው፡፡እናቷ እና አንድያ ልጆ የሚኖሩበት ቤት ባልታወቁ ሰዎች ተቃጥሎባቸው..ጥሪት አልባ ሆነው ባዶ እጃቸውን በመቅረታቸው ሰው እጅ ላይ ለዛውም በባዕድ ሰው ድጋፍ ስር እንደሆኑ ከሰማች ጊዜ አንስቶ በውጧ ሰላም አልነበራትም…
አደጋውን በሰማች በማግስቱ ሀያ ሺ ብር በባንክ ልካላቸው መላኳንም እንዲያውቁት አድርጋ ነበር..ግን የደረሳት ምላሽ ጭራሽ ብሶቷን የሚጨምር ነበር፡፡
‹‹ያንቺን ሽራፊ ሳንቲም አንፈልግም..እኛ በእግዚዘብሄር ጥበቃ ስር ነው ያለነው…ለእኛ አታስቢ… ብርሽን መልሰሽ አውጪው….እና ለራስሽው ተጠቀሚው›› ብለው ነበር የመለሱላት፡፡
ከዛ ቡኃላ ነው በጣም ከተቀየሟት እናቷ እና ልጆ ጋር ፊት ለፊት ለመጋፈጥ ወሰና ወደ ሻሸመኔ እየተጓዘች ያለችው..ለዚህም ድጋፍ እና ወኔ ይሆናት ዘንድ ከጐኗ አቤልን አስከትላለች…..
ዝዋይን እስኪያልፉ አቤል መኪናውን እያሽከረከረ እሷ እንቅልፍ የወሰዳት አስመስላ ወንበሯን ወደኃላ ለጥጣ አይኖን በመጨፍን በትካዜ ስትናውዝ ነበር የቆየችው ..አሁን ግን ለመጀመሪሪያ ጊዜ እንደመባነን እና እንደመነቃቃት ብላ መናገር ጀመረች.. ‹‹አብዬ..አሁን ፊት ለፊታቸው ስጋፈጣቸው እንዴት ይቀበሉኝ ይመስልሀል?››
‹‹ቀላል አይሆንም… ግን እወነታውን ከመጋፈጥ ውጭ ሌላ መንገድ የለሽም.››
‹‹እንዴት አድርጌ ነው የምጋፈጠው? ከሚጠሉህ ሰዎች ፊት ለፊት መቆም እኮ በጣም ከባድ ነገር ነው››
‹‹ይህውልሽ ፈፅሞ እንደዚህ እዳታስቢ… አሁን የምትሄጂው ወደሚጠሉሽ ሰዎች ጋር ሳይሆን በጣም የሚወዱሽ እና የሚያፈቅሩሽ ግን ለጊዜው ወደተቀየሙሽ ያንቺ ወደሆኑ ሰዎች ጋር ነው ፡፡››
‹‹አይ አንተ……. እስኪ እንደእዛ ቀለል እያደረግክ ብርታት እና ወኔ ስጠኝ››
‹‹አይ ባዶ ወኔ እየሰጠውሽ አይደፈለም..የሚሰማኝን እውነት እየነገርኩሽ ነው… በጣም ይጠሉኛል ብለሽ በውስጥሽ ጨላማ ሀሳብ ይዘሽማ ከሄድሽ ጥሩ ነገር አይገጥምሽም..ምንም ቢሆን እኮ ለእናትሽም ልጆ..ለልጅሽም እናቷ ነሽ…እርግጠኛ ነኝ በዚህ ምድር ላንቺ ከእነሱ በላይ የምታስቢላቸው ….እነሱም ካንቺ በላይ የሚጨነቁለት እና ክፍውን መስማት የማይፈልጉት ሌላ ሰው ያለ አይመስለኝም….በመሀከላችሁ ቅያሜ እንጂ ስር የሰደደ ጥላቻ ሊኖር አይችልም..፡፡እስኪ ነገሩን በራስሽ ገልብጠሸ አስቢው …አሁን ልጅሽ የፈለገ ነገር ብታጠፋ..ምንም ነገር ብትበድልሽ አምርረሽ ልትጠያት ትችያት ነበር..?እናትሽንስ?››
‹‹እሱን እንኳን እንዴት ብዬ?››
‹‹እኮ በቃ እነሱም እንደዛ ናቸው..››
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ሻሸመኔ ሲደርሱ 11 ሰዓት ሆኖ ነበር…ወዲያው ለሄለን ደወለላት
‹‹ሄሎ››
‹‹ሄሎ ሄለን ሰላም ነሽ››
‹‹አለውልህ አቤል ..አንተስ ?››
‹‹እኔ ሰላም ነኝ መጥቼ ነበር…ሰፈራችሁ የት ነው?››
‹‹ሰፈራችን…››ግራ ገባት እቤታቸውን ትንገረውና ይምጣ ወይስ እሱ ወዳለበት ሄዳ ታግኘው?
‹‹ምነው ድምጽሽ ጠፋ?››
‹‹ሰፈሩን በምልክት ብነግርህ ላታውቀው ትችላልህ ብዬ ሰግቼ ነው..ወይ ለምን አንተ ያለህበትን ቦታ አትነግረኝምና አኔ አልመጣም?››
‹‹አይ ግድ የለሽም አንቺ ብቻ ትክክለኛ የቤታችሁን አድራሻ ስጪኝ …ሌላውን ለእኔ ተይው..አያትሽንም ማግኘት ስላለብኝ እቤት ነው መምጣት የምፈልገው..መቼስ አባ ቅር የሚላቸው አይመስለኝም?››
‹‹ኸረ በፍጹም ››
‹‹እሺ እንግዲያው ንገሪኛ››
‹‹በዝርዝር የነገረችውን በማስታወሻው ላይ መዝግቦ እንደጨረሰ ተሰናብቷት ስልኩን ዘጋው…ሮዝን አስከትሎ እንደመጣ አልነገራም ..ይህንን ያደረገው ቀድሞ ነገር ላለማበለሻሸት ነው፡፡››
‹‹አሁን ቀጥታ እንሂድ አይደል?››ጠየቃት ወደ ሮዝ ዞሮ
‹‹ተው ይቅርብኝ….. መጀመሪያ አንተ ብቻህን ሂድና ነገሩን አጣራ ››
‹‹ኸረ ተይ ዝም ብለሽ ተጋፈጪው ..ካልደፈረሰ አይጠራም ሲባል አልሰማሽም››
‹‹ ተው እኔ አልፈልግም…››
‹‹እሺ እንሂድና አንቺ መኪናው ውስጥ ትጠብቂኛለሽ..እኔ ብቻዬን እንደመጣው አስመስዬ እገባለው ሁኔታውን አይቼ አሪፍ ከሆነ ትቀላቀይናለሽ ካለበለዚያም ዛሬን አድረን ነገ ተነገወዲያ ሌላ ዘዴ እንፈልጋለን››
‹‹ባይሆን ይሄኛው ዘዴህ ይሻላል››አለችው …ተንፈስ እንደማለት ብላ..አቤልም ያቆመውን መኪና አስነስቶ ነዳው….. የጠቆመችውን ቤት ለማግኘት ብዙም አልተቸገረም..በተስማሙት መሰረት መኪናዋን እራቅ አድርጐ አቆማት እና ሮዝን ጭብጥ እንዳለች መኪናው ውስጥ ትቷት ወደአባ ቤት አምርቶ አንኳኳ …...ራሷ ሄለን ነበረች በሩን የከፈተችለት..በደመቀ ፈገግታ እና በተፍለቀለቀ የፈንጠዝያ ስሜት ነበር ተቀብላ ወደ ውስጥ እንዲገባ የጋበዘችው..ምንም አልተግደረደረም ዘልቆ ወደውስጥ ገባ…ሳሎን ሲደርስ የሄለንን አያት ብቻ ሳይሆን አባ ሽፍንፍንንም ጭምር ነበር ያገኛቸው…ሄለን ከሁለቱም ጋር አስተዋቀቻቸው..ለእናትዬው ስለማንነቱ በጆሮአቸው ሔዳ ሹክ አለቻው..በፊታቸው ላይ ምንም አይነት የስሜት መለዋወጥ አልታየባቸውም…ሄለን ወዲያው ቡና ለማፍላት ጉድ ጉድ ማለት ጀመረች እናትዬውም መክሰስ ነገር ለማዘጋጀት ወደ ኩሽና ሄዱ
‹‹ከአዲስ አበባ ነው የመጣውት አልከኝ?››አሉት አባ
‹‹አዎ አባቴ…እነሄለን በጣም ወዳጆቼ ናቸው የደረሰባቸውን አደጋ ከሰማውበት ቀን አንስቶ ከዛሬ ነገ እመጣለው ስለ እስከዛሬ ቆየው››ብሎ መለሰላቸው …መልሱ በግርምት የታጀበ ነበር..በዚህ ሙቀት ወቅት ለዛውም እቤታቸው ውስጥ ሆነው መላ አካላቸውን ፊታቸውንም ሳይቀር በዚህ መልክ ሸፍነው የፈረንጆችን
‹‹አይደለም…. በፍፅም አይደለም….አኔ በእዚህ ትውውቃችን ምን ያህል ደስተኞች እንደሆንኩ አታውቅም ….እዚህ ቤትህ ስመጣ ለፒያኖ ለመለማመድ ብቻ እንዳይመስልህ…..ልክ ታላቅ ወንድሜ ቤት እንደምመጣ አይነት እየተሰማኝ ነው ምመጣው..መቼም ይሄንን ግንኙነታችንን ማቋረጥ አልፈልግም …ሁሌ ከስርህ የማትጠፋ ታናሽ እህትህ መሆን ነው የምፈልገው ….›› አለችው በፈገግታ
‹‹አመሰግናለው››አላት በእርካታ…አዎ አሁን ቀስ በቀስ የወጣትነት አማኝ ልቧን በመሸርሸር ወደ ሚፈልገው መስመር እያስገባት መሆኑን በመረዳቱ ለስኬታማነቱ እራሱን በውስጡ አደነቀ…..
‹‹እሺ ወንድም ጋሼ አሁን በጣም መሸ ልሂድ›› ብላ ከመቀመጫዋ ተነሳች….
‹‹አንቺ አሪፍ ስምነው ያወጣሺልኝ… ወንድም ጋሼ ነው ያልሺኝ?››እያለ ከመቀመጫው ተነሳ እና እጁን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርጎ ውጭ ድረስ ሸኛት ‹‹መልካም ለሊት… መልካም ህልም ››በማለት ወደ ራሱ ጐትቶ ግንባሯን ሳመና በቆመችበት ጥሎት ፊቱን አዙሮ ወደቤት ተመለሰ..
እሷም ልትገምታቸው ላልቻለቻቸው ሴኮንዶች ባለችበት ፈዛ ቆመች..የሆነ የማታውቀው ስሜት ነው የተሰማት ..ከዚህ በፊት እንዲህ ከሰውነቷ ልጥፍ ብሎባትም የሳማት ሰው መኖሩን አታስታውስም……. በጣም ያስገረማት ደገሞ በእሱ መሳሙ ሳይሆን መሳሙን ተከትሎ በውስጧ የተፈጠረባት ምንነቱን መለየት ያልቻለችው ግራ አጋቢ ስሜት ነው...ብዥ ነው ያለባት….እንዴት ከተገተረችበት ተንቀሳቅሳ ዞራ እቤቷ እንደደረሰች ራሱ አታውቅም
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ሮዝ እና አቤል ወደ ሻሸመኔ እየሄዱ ነው፡፡በህዝብ ትራንስፖር አይደለም የሚጓዙት….ሮዝ በተከራየችው የቤት መኪና በአቤል ሾፋሪነት ነው፡፡
ሮዝ በዚህ ሰዓት ወደ ሻሸመኔ የምትጓዘው ለመዝናንተ ወይም ለሽርሽር አይደለም…ተገዳ ነው…የምታደርገው ጠፍቷት ነው፡፡እናቷ እና አንድያ ልጆ የሚኖሩበት ቤት ባልታወቁ ሰዎች ተቃጥሎባቸው..ጥሪት አልባ ሆነው ባዶ እጃቸውን በመቅረታቸው ሰው እጅ ላይ ለዛውም በባዕድ ሰው ድጋፍ ስር እንደሆኑ ከሰማች ጊዜ አንስቶ በውጧ ሰላም አልነበራትም…
አደጋውን በሰማች በማግስቱ ሀያ ሺ ብር በባንክ ልካላቸው መላኳንም እንዲያውቁት አድርጋ ነበር..ግን የደረሳት ምላሽ ጭራሽ ብሶቷን የሚጨምር ነበር፡፡
‹‹ያንቺን ሽራፊ ሳንቲም አንፈልግም..እኛ በእግዚዘብሄር ጥበቃ ስር ነው ያለነው…ለእኛ አታስቢ… ብርሽን መልሰሽ አውጪው….እና ለራስሽው ተጠቀሚው›› ብለው ነበር የመለሱላት፡፡
ከዛ ቡኃላ ነው በጣም ከተቀየሟት እናቷ እና ልጆ ጋር ፊት ለፊት ለመጋፈጥ ወሰና ወደ ሻሸመኔ እየተጓዘች ያለችው..ለዚህም ድጋፍ እና ወኔ ይሆናት ዘንድ ከጐኗ አቤልን አስከትላለች…..
ዝዋይን እስኪያልፉ አቤል መኪናውን እያሽከረከረ እሷ እንቅልፍ የወሰዳት አስመስላ ወንበሯን ወደኃላ ለጥጣ አይኖን በመጨፍን በትካዜ ስትናውዝ ነበር የቆየችው ..አሁን ግን ለመጀመሪሪያ ጊዜ እንደመባነን እና እንደመነቃቃት ብላ መናገር ጀመረች.. ‹‹አብዬ..አሁን ፊት ለፊታቸው ስጋፈጣቸው እንዴት ይቀበሉኝ ይመስልሀል?››
‹‹ቀላል አይሆንም… ግን እወነታውን ከመጋፈጥ ውጭ ሌላ መንገድ የለሽም.››
‹‹እንዴት አድርጌ ነው የምጋፈጠው? ከሚጠሉህ ሰዎች ፊት ለፊት መቆም እኮ በጣም ከባድ ነገር ነው››
‹‹ይህውልሽ ፈፅሞ እንደዚህ እዳታስቢ… አሁን የምትሄጂው ወደሚጠሉሽ ሰዎች ጋር ሳይሆን በጣም የሚወዱሽ እና የሚያፈቅሩሽ ግን ለጊዜው ወደተቀየሙሽ ያንቺ ወደሆኑ ሰዎች ጋር ነው ፡፡››
‹‹አይ አንተ……. እስኪ እንደእዛ ቀለል እያደረግክ ብርታት እና ወኔ ስጠኝ››
‹‹አይ ባዶ ወኔ እየሰጠውሽ አይደፈለም..የሚሰማኝን እውነት እየነገርኩሽ ነው… በጣም ይጠሉኛል ብለሽ በውስጥሽ ጨላማ ሀሳብ ይዘሽማ ከሄድሽ ጥሩ ነገር አይገጥምሽም..ምንም ቢሆን እኮ ለእናትሽም ልጆ..ለልጅሽም እናቷ ነሽ…እርግጠኛ ነኝ በዚህ ምድር ላንቺ ከእነሱ በላይ የምታስቢላቸው ….እነሱም ካንቺ በላይ የሚጨነቁለት እና ክፍውን መስማት የማይፈልጉት ሌላ ሰው ያለ አይመስለኝም….በመሀከላችሁ ቅያሜ እንጂ ስር የሰደደ ጥላቻ ሊኖር አይችልም..፡፡እስኪ ነገሩን በራስሽ ገልብጠሸ አስቢው …አሁን ልጅሽ የፈለገ ነገር ብታጠፋ..ምንም ነገር ብትበድልሽ አምርረሽ ልትጠያት ትችያት ነበር..?እናትሽንስ?››
‹‹እሱን እንኳን እንዴት ብዬ?››
‹‹እኮ በቃ እነሱም እንደዛ ናቸው..››
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ሻሸመኔ ሲደርሱ 11 ሰዓት ሆኖ ነበር…ወዲያው ለሄለን ደወለላት
‹‹ሄሎ››
‹‹ሄሎ ሄለን ሰላም ነሽ››
‹‹አለውልህ አቤል ..አንተስ ?››
‹‹እኔ ሰላም ነኝ መጥቼ ነበር…ሰፈራችሁ የት ነው?››
‹‹ሰፈራችን…››ግራ ገባት እቤታቸውን ትንገረውና ይምጣ ወይስ እሱ ወዳለበት ሄዳ ታግኘው?
‹‹ምነው ድምጽሽ ጠፋ?››
‹‹ሰፈሩን በምልክት ብነግርህ ላታውቀው ትችላልህ ብዬ ሰግቼ ነው..ወይ ለምን አንተ ያለህበትን ቦታ አትነግረኝምና አኔ አልመጣም?››
‹‹አይ ግድ የለሽም አንቺ ብቻ ትክክለኛ የቤታችሁን አድራሻ ስጪኝ …ሌላውን ለእኔ ተይው..አያትሽንም ማግኘት ስላለብኝ እቤት ነው መምጣት የምፈልገው..መቼስ አባ ቅር የሚላቸው አይመስለኝም?››
‹‹ኸረ በፍጹም ››
‹‹እሺ እንግዲያው ንገሪኛ››
‹‹በዝርዝር የነገረችውን በማስታወሻው ላይ መዝግቦ እንደጨረሰ ተሰናብቷት ስልኩን ዘጋው…ሮዝን አስከትሎ እንደመጣ አልነገራም ..ይህንን ያደረገው ቀድሞ ነገር ላለማበለሻሸት ነው፡፡››
‹‹አሁን ቀጥታ እንሂድ አይደል?››ጠየቃት ወደ ሮዝ ዞሮ
‹‹ተው ይቅርብኝ….. መጀመሪያ አንተ ብቻህን ሂድና ነገሩን አጣራ ››
‹‹ኸረ ተይ ዝም ብለሽ ተጋፈጪው ..ካልደፈረሰ አይጠራም ሲባል አልሰማሽም››
‹‹ ተው እኔ አልፈልግም…››
‹‹እሺ እንሂድና አንቺ መኪናው ውስጥ ትጠብቂኛለሽ..እኔ ብቻዬን እንደመጣው አስመስዬ እገባለው ሁኔታውን አይቼ አሪፍ ከሆነ ትቀላቀይናለሽ ካለበለዚያም ዛሬን አድረን ነገ ተነገወዲያ ሌላ ዘዴ እንፈልጋለን››
‹‹ባይሆን ይሄኛው ዘዴህ ይሻላል››አለችው …ተንፈስ እንደማለት ብላ..አቤልም ያቆመውን መኪና አስነስቶ ነዳው….. የጠቆመችውን ቤት ለማግኘት ብዙም አልተቸገረም..በተስማሙት መሰረት መኪናዋን እራቅ አድርጐ አቆማት እና ሮዝን ጭብጥ እንዳለች መኪናው ውስጥ ትቷት ወደአባ ቤት አምርቶ አንኳኳ …...ራሷ ሄለን ነበረች በሩን የከፈተችለት..በደመቀ ፈገግታ እና በተፍለቀለቀ የፈንጠዝያ ስሜት ነበር ተቀብላ ወደ ውስጥ እንዲገባ የጋበዘችው..ምንም አልተግደረደረም ዘልቆ ወደውስጥ ገባ…ሳሎን ሲደርስ የሄለንን አያት ብቻ ሳይሆን አባ ሽፍንፍንንም ጭምር ነበር ያገኛቸው…ሄለን ከሁለቱም ጋር አስተዋቀቻቸው..ለእናትዬው ስለማንነቱ በጆሮአቸው ሔዳ ሹክ አለቻው..በፊታቸው ላይ ምንም አይነት የስሜት መለዋወጥ አልታየባቸውም…ሄለን ወዲያው ቡና ለማፍላት ጉድ ጉድ ማለት ጀመረች እናትዬውም መክሰስ ነገር ለማዘጋጀት ወደ ኩሽና ሄዱ
‹‹ከአዲስ አበባ ነው የመጣውት አልከኝ?››አሉት አባ
‹‹አዎ አባቴ…እነሄለን በጣም ወዳጆቼ ናቸው የደረሰባቸውን አደጋ ከሰማውበት ቀን አንስቶ ከዛሬ ነገ እመጣለው ስለ እስከዛሬ ቆየው››ብሎ መለሰላቸው …መልሱ በግርምት የታጀበ ነበር..በዚህ ሙቀት ወቅት ለዛውም እቤታቸው ውስጥ ሆነው መላ አካላቸውን ፊታቸውንም ሳይቀር በዚህ መልክ ሸፍነው የፈረንጆችን
👍3
የገና አባትን መስለው ሲያያቸው ለምን አይገረም..እንዲህ አይነት አለባበስ የሚለብስ ቄስም ሆነ መለኩሴ በህይወት ዘመኑ ገጥሞት አያውቅም…በጣም ነው ትኩረቱን የሳቡት..‹‹ቆንጆ ገፃባህሪ ይወጣቸዋል›› ሲል ወሰነ እና መላ ነገራቸውን በአእምሮ መዝግቦ ለመያዝ በጥሞና እያጠናቸው ጭውውቱን ቀጠለ
‹‹አይ ልጄ ኑሮ መች ፋታ ይሰጣል ብለህ ነው..እንኳን ትርምስ የበዛበት የአዲስ አበባ ኑሮ ይቅርና እዚህ እኛ ጋር እራሱ ወከባ ነው…በዚህ ዘመን ህይወት የጽሞና ጊዜ ራሱ ልትሰጠን እየፈቀደች አይደለም…..››
‹‹እውነቷትን ነው አባ …ሰው ከራሱ አልፎ ለሌላው ችግር መድረስ እያቃተው ነው…ብቻ እንኳንም እርሶን ጣለላቸው እንጂ …››
‹‹አይ ልጄ እኔማ ምን አደረግኩላቸው ብለህ ነው..እንደውም በተቃራኒው የእኔ ብቸኝነት ለመቅረፍ ሲያስብ እነሱን ጣለልኝ..የቤቴ ድምቀት ሆነውልኛል…››በዚህን ጊዜ ሄለን የቆላችውን ቡና ልትወቅጥ ከሳሎን ይዛ ስትወጣ አያትዬው ደግሞ የተሰራውን መክሰስ ይዘው መጡና አቀረቡ… አባ ባረኩና አብረው መብላት ጀመሩ.. የአባ እና የአቤል መግባባት የረጂም ጊዜ የሚተዋወቁ ወዳጆች ነው የሚያስመስላቸው..ሄለን እንኳን ተገረማለች..መክሰሱ ተበልቶ እንደተጠናቀቀ እና መአዱ እንደተነሳ… ሄለን የቀዳችውን ቡና ለሶስቱም አቀረበችላቸው…በጫወታ እያዋዙ ጠጥተው ሲኒውን መለሱላት ደገመቻቸው..በዚህን ጊዜ ሰዓቱ 12፡15 ሆኖ ነበር ..ሄለን ቀልቦ ያለው ኩማንደሩ ቤት ነው..ናፍቋታል…ይሄኔ ስራውን ጥሎ እሷን ፒያኖ ለማሰልጠን እቤት ቁጭ ብሎ እየጠበቃት ነው…
‹‹አቤል ይቅርታ ከአባ ጋር የያዝከው ጫወታ የተመቸህ ይመስለኛል…እኔ ጥዬህ ልሄድ ነው››አለችው ቅር እያላትማ እያፈረችም
‹‹የት ልትሄጂ ነው?››ጠየቃት ግራ ተጋብቶ
‹‹የፒያኖ ልምምድ አለብኝ ..እንደውም 15 ደቂቃ አርፍጄያለው››
‹‹ግድ የለለሽም ሂጂ ሳምንቱን ሙሉ እዚህ ነኝ …ማታ ደውልልሻለው››አላት ተሰናብታው ፈጥና ግቢውን ለቃ ወጣች… በጓሮ በኩል ዞራ ከጀራባ ባለው ጊቢ ወደሚገኘው የኩማደሩ ቤት አመራች
ሄለን ወጥታ እንደሄደችም..‹‹ተጫወቱ ኩሽና ትንሽ ስራ ይዤ ነው›› ብለው አያትዬውም ለቀውላቸው ወጡ
..አቤል ይሄን አጋጣሚ ሊጠቀምነበት ፈለገ‹‹አባ እንደው ደፈረኝ አይበሉኝ እና አንድ ነገር ላማክሮት ነበር››
‹‹ልጄ አባትህ ነኝ ቀጥል››ሲሉ አበረታቱት
‹‹ሮዝን ያውቋታል?››
‹‹ሮዝ እሮዝ››
‹‹የሄለን እናት ..አዲስአበባ ያለችው››
‹‹አዎ እናቷ አንድ ሁለቴ ስለእሷ አጫውተውኛል….ለአንተም ወዳጅህ ነች መሰለኝ…?እንደው አትታዘበኝ እና እኔ ስለ እሷ ልጅ ሳስብ እንዲሁ ታሳዝነኛለች››
የአባ ንግግር ለአቤል ደስታ ፈጠረለት… ልክ እንደ አረንጓዴ የመንገድ መብራት ወደፊት እንዲቀጥል አበረታታው.. ‹ቢያውቋት ደግሞ ይገርሞታል…በጣም የምታዛዝን …ማንም ያልተረዳላትን ብዙ መከራ ብቻዋን አፍና የኖረች ምስኪን ነች››
‹‹አዎ እኔም እንደእዛ ነው የሚሰማኝ››
‹‹እና አባ ይህቺ ሮዝ..››
‹‹ሮዝ ምን ሆነች?››
‹‹የእናቷ እና የልጆ ጉዳይ በጣም አሳቧታል››
‹‹አልገባኝ…እንደምታየው እነሱ በጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ያሉት….ምንም የሚያሳስብ ጉዳይ ያለ አይመስለኝም››
‹‹አይ አባ እሷን ሰላም የነሳት ከእነሱ ጋር ጥል ላይ ስለሆነች ነው …መታረቅ ትፈልጋለች… ይቅር እንዲሏት ትሻለች››
‹‹አይ ልጄ ታዲያ እነሱን ማስታረቅ እኮ የእኔ ስራ እና ኃላፊነት ነበር …አንተም መልካምም አልሰራህ … ይዘሀት መጥተህ ቢሆን እኮ ..››
ከአፋቸው ነጠቀቸውና ‹‹መጥታለች እኮ ውጭ መኪና ውስጥ ነች ያለችው››
‹‹የት አልከኝ?››
‹‹እዚሁ እናንተው ሰፈር ከግቢው ውጭ ..ዝም ብሎ መግባ ፈርታ እና ተሳቃ ነው››
‹‹ይሄን ሁሉ ሰዓት ውጭ አስቀምጥኸት ነወ? ምነው ልጄ እግዜር የማይወደውን ስራ ነው የሰራሀው..በል ሂድና አምጣት››
‹‹ግን አባ››
‹‹ምንም ግን የለም አምጣት ብዬኸለው አምጣት…››
አቤል ትዛዛቸውን አክብሮ ሮዝን ሊያመጣት ቤቱን ለቆ ወጣ...
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
‹‹አይ ልጄ ኑሮ መች ፋታ ይሰጣል ብለህ ነው..እንኳን ትርምስ የበዛበት የአዲስ አበባ ኑሮ ይቅርና እዚህ እኛ ጋር እራሱ ወከባ ነው…በዚህ ዘመን ህይወት የጽሞና ጊዜ ራሱ ልትሰጠን እየፈቀደች አይደለም…..››
‹‹እውነቷትን ነው አባ …ሰው ከራሱ አልፎ ለሌላው ችግር መድረስ እያቃተው ነው…ብቻ እንኳንም እርሶን ጣለላቸው እንጂ …››
‹‹አይ ልጄ እኔማ ምን አደረግኩላቸው ብለህ ነው..እንደውም በተቃራኒው የእኔ ብቸኝነት ለመቅረፍ ሲያስብ እነሱን ጣለልኝ..የቤቴ ድምቀት ሆነውልኛል…››በዚህን ጊዜ ሄለን የቆላችውን ቡና ልትወቅጥ ከሳሎን ይዛ ስትወጣ አያትዬው ደግሞ የተሰራውን መክሰስ ይዘው መጡና አቀረቡ… አባ ባረኩና አብረው መብላት ጀመሩ.. የአባ እና የአቤል መግባባት የረጂም ጊዜ የሚተዋወቁ ወዳጆች ነው የሚያስመስላቸው..ሄለን እንኳን ተገረማለች..መክሰሱ ተበልቶ እንደተጠናቀቀ እና መአዱ እንደተነሳ… ሄለን የቀዳችውን ቡና ለሶስቱም አቀረበችላቸው…በጫወታ እያዋዙ ጠጥተው ሲኒውን መለሱላት ደገመቻቸው..በዚህን ጊዜ ሰዓቱ 12፡15 ሆኖ ነበር ..ሄለን ቀልቦ ያለው ኩማንደሩ ቤት ነው..ናፍቋታል…ይሄኔ ስራውን ጥሎ እሷን ፒያኖ ለማሰልጠን እቤት ቁጭ ብሎ እየጠበቃት ነው…
‹‹አቤል ይቅርታ ከአባ ጋር የያዝከው ጫወታ የተመቸህ ይመስለኛል…እኔ ጥዬህ ልሄድ ነው››አለችው ቅር እያላትማ እያፈረችም
‹‹የት ልትሄጂ ነው?››ጠየቃት ግራ ተጋብቶ
‹‹የፒያኖ ልምምድ አለብኝ ..እንደውም 15 ደቂቃ አርፍጄያለው››
‹‹ግድ የለለሽም ሂጂ ሳምንቱን ሙሉ እዚህ ነኝ …ማታ ደውልልሻለው››አላት ተሰናብታው ፈጥና ግቢውን ለቃ ወጣች… በጓሮ በኩል ዞራ ከጀራባ ባለው ጊቢ ወደሚገኘው የኩማደሩ ቤት አመራች
ሄለን ወጥታ እንደሄደችም..‹‹ተጫወቱ ኩሽና ትንሽ ስራ ይዤ ነው›› ብለው አያትዬውም ለቀውላቸው ወጡ
..አቤል ይሄን አጋጣሚ ሊጠቀምነበት ፈለገ‹‹አባ እንደው ደፈረኝ አይበሉኝ እና አንድ ነገር ላማክሮት ነበር››
‹‹ልጄ አባትህ ነኝ ቀጥል››ሲሉ አበረታቱት
‹‹ሮዝን ያውቋታል?››
‹‹ሮዝ እሮዝ››
‹‹የሄለን እናት ..አዲስአበባ ያለችው››
‹‹አዎ እናቷ አንድ ሁለቴ ስለእሷ አጫውተውኛል….ለአንተም ወዳጅህ ነች መሰለኝ…?እንደው አትታዘበኝ እና እኔ ስለ እሷ ልጅ ሳስብ እንዲሁ ታሳዝነኛለች››
የአባ ንግግር ለአቤል ደስታ ፈጠረለት… ልክ እንደ አረንጓዴ የመንገድ መብራት ወደፊት እንዲቀጥል አበረታታው.. ‹ቢያውቋት ደግሞ ይገርሞታል…በጣም የምታዛዝን …ማንም ያልተረዳላትን ብዙ መከራ ብቻዋን አፍና የኖረች ምስኪን ነች››
‹‹አዎ እኔም እንደእዛ ነው የሚሰማኝ››
‹‹እና አባ ይህቺ ሮዝ..››
‹‹ሮዝ ምን ሆነች?››
‹‹የእናቷ እና የልጆ ጉዳይ በጣም አሳቧታል››
‹‹አልገባኝ…እንደምታየው እነሱ በጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ያሉት….ምንም የሚያሳስብ ጉዳይ ያለ አይመስለኝም››
‹‹አይ አባ እሷን ሰላም የነሳት ከእነሱ ጋር ጥል ላይ ስለሆነች ነው …መታረቅ ትፈልጋለች… ይቅር እንዲሏት ትሻለች››
‹‹አይ ልጄ ታዲያ እነሱን ማስታረቅ እኮ የእኔ ስራ እና ኃላፊነት ነበር …አንተም መልካምም አልሰራህ … ይዘሀት መጥተህ ቢሆን እኮ ..››
ከአፋቸው ነጠቀቸውና ‹‹መጥታለች እኮ ውጭ መኪና ውስጥ ነች ያለችው››
‹‹የት አልከኝ?››
‹‹እዚሁ እናንተው ሰፈር ከግቢው ውጭ ..ዝም ብሎ መግባ ፈርታ እና ተሳቃ ነው››
‹‹ይሄን ሁሉ ሰዓት ውጭ አስቀምጥኸት ነወ? ምነው ልጄ እግዜር የማይወደውን ስራ ነው የሰራሀው..በል ሂድና አምጣት››
‹‹ግን አባ››
‹‹ምንም ግን የለም አምጣት ብዬኸለው አምጣት…››
አቤል ትዛዛቸውን አክብሮ ሮዝን ሊያመጣት ቤቱን ለቆ ወጣ...
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ሀያ_አራት
:
✍ድርሰት፦በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...አቤል ያገኘውን እድል ባለማመን በጥድፊያ ነበር ወደ ሮዝ የሄደው..ኩምሽሽ ብላ መኪና ውስጥ እንደተቀመጠች ነበር ያገገኛት
‹‹ቆየውብሽ አይደል?››
‹‹የምዕተ ዓመት ያህል ነዋ…በዛ ላይ ሄለን ከግቢው ወጥታ በዛች ቀጭን መንገድ ወደ ጀርባ በኩል ስትሄድ ሳያት ምን ተፈጠረ ብዬ ነፍሴ ልትወጣ ነበር….ስልክህን ስደውልልህ ደግሞ አታነሳም››አለችው ስልችት እንዳላት በሚያሳብቅ እና እንባ በተናነቀው ስሜት
‹‹በይ አሁን እንግባ››
‹‹ወዴት ነው የምንገባው?››
‹‹ወደ ውስጥ ነዋ..አንቺ እኚ ቄስ እግዚያብሄር የባረካቸው ናቸው …ገና አብራርቼ እንኳን ስለመጣንበት ጉዳይ ሳልነግራቸው ነው የተረዱኝ…እንደውም አንቺን እዚህ ውጭ አስቀምጪ ይህን ያህል በመቆየቴ በጣም ነው የገሰጹኝ…እሷን ብቻ ይዘኸት ና …እርቁን ለእኔ ተወው ብለውኛል››
‹‹እውነትህን ነው?›› በጉጉት እና በተስፋ ጠየቀችው
‹‹አዎ ተነሽ እንግባ…ለመሆኑ እማዬ ሰላም ነች››
‹‹ሰላም ናቸው… አሁን ልታያቸው አይደል?››
‹‹ወይ አቤልዬ በጣም ነው የፈራውት… ሽንቴ ሁሉ ሊያመልጠኝ ነው››አለች መኪናውን ለቃ ወደ ውጭ እየወጣች
‹‹አይዞሽ ጠንከር በይ›› ብሎ ስትንገዳገድ ደገፋና የመኪናውን በራፍ ዘግቶ እና ቆልፎ ይዞት ወደ አባ ሽፍንፍን ቤት ተጓዘ ..ልክ እቤት ደርሰው የሳሎንን በራፍ አልፋው ወደ ውስጥ እደገቡ እናትዬው በተቀመጡበት ቀና ብለው ሲያዩት እና ልጃቸው ሮዝ መሆኖን ሲያውቁ‹‹ወይኔ ጉዴ!!!›› ብለው ጩኹ….ጩኸታቸው ሮዝን ብቻ ሳይሆን ሌሎችንም አስደነገጠ.
‹‹ግቡ.. ግቡ ››በማለት አባ አቤል እና ሮዝ ተረጋግተው ወደውስጥ እንዲገቡ አበረታቶቸው…
‹‹እማዬ›› አለች ሮዝ ወደውስጥ በዝግታ እየመጣች
‹‹እማዬ አትበይኝ አንቺ ጉድ!! ››አሏት በተቀመጡበት ደንግጠው አፋቸውን በእጃቸው እንደያዙ
‹‹እማ ባክሽ ናፍቀሺኛል …በጣም ናፍቀሺኛል..››አለቻቸው…እናትዬው ፀጥ እንዳሉ ነው… እንባቸው በጉንጫቸው ላይ ተንኳለለ.. ሮዝ ተንደርድራ ወደተቀመጡበት ሄደችና እግራቸው ላይ ተዘረገፈች
‹‹እባክሽ እማ..እኔስ ማን አለኝ? ይቅር በይኝ ..እንደድሮሽ እንደልጅነቴ ተቆጥተሺኝ ና ገርፈሺኝ መልሰሽ አባበብይኝ…እማ ጠረንሽ ናፍቆኛል..እማ ትንፋሽሽ ርቦኛል…››አባ ሽፍንፍን በተቀመጡበት አቤል እንደቆመ ሁኔታውን እየተከታተሉ ነው፡፡
እናትዬው ዝም እንዳሉ ነው….. የሚያደርጉት ግራ ገብቷቸዋል…በዚህ ጊዜ አባ ሽፍንፍን መስቀላቸውን ከኪሳቸውን አወጡና ቆሙ ‹‹እንግዲህ ሰው ሆኖ ለዛውም ልጅ ሆኖ የማያጠፋ የለም…በቃ ይቅር በሏት ››ሲሉ መሸምገላቸውን ጀመሩ
‹‹አባ እርሶ እኮ ስለእሷ ሁሉንም አያውቁም››
‹‹ግድ የለም ሁሉንም ማወቅ አያስፈልገኝም..ግን እርግጠኛ ነኝ ከይቅርታ በላይ የሆነ በደል የለም..በዛ ላይ እናት በልጆ ላይ አትጨክንም..››
‹‹እርሱማ እንዴት ብዬ ጨክናለው?››
‹‹እግዜር ያክብሮት ..እመብርሀን እድሜ ትስጦት›› አባ መረቁ
‹‹በይ ተነሽ ››አሏት እናቷ ጭንቅላቷን እያሻሹ…
‹‹ይቅር አልሺኝ እማ..በቃ ታረቅን?››ባለማን እና በመነፍረቅ ጠየቀች
‹‹ተነሺ አልኩሽ እኮ…››ብለው ተከሻውና አነሱ እና ቀና እንድትል አደረጐትና በስስት እና በናፍቆት ጉንጯን ለመሳም ወደ እሷ በተሳቡበት ደቂቃ ሄለን ለፒያኖ ልምምድ የቀረውን ኩማደሩን ጥበቃ አሰልችቶት በመመለስ የሳሎኑን በራፍ ከፍታ ገባች..ፊት ለፊቷ የሚከወነውን ነገር ስታይ በድንዛዜ ሀውልት ሆና ነው የቋመችው፡፡
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ሮዝ እና አቤል ሻሸመኔ አባ ሽፍንፍን ቤት ከከተሙ ሶስት ቀን አልፎቸዋል…በእነዚህ ቀናቶች ውስጥ የሮዝ ስሜት ግምሽ ደስታ ግማሽ ሀዘን….ግማሽ ሳቅ ግማሽ ለቅሶ ሁኖ ነው የሰነበተው፡፡ይህ የሆነበት ምክንያት ባላሰበችው ፍጥነት ከእናቷ ይቅርታን አግኝታ የውስጥ ሰላም ብታገኝም…ልጇ ሄለን ግን እስከአሁን አሻፈረኝ እንዳለቻት ነው፡፡በዚህ ክስተት አንድ እውነት ገብቷታል…እናትነት እና ልጅነት መካከል ያለውን ልዩነት…እናትነት የፍቅር ጥግ መግለጫ ነው..እናትነት የይቅር ባይነት የመጨረሻ ማሳያ ነው…ለዚህ ነው ከእናቷ የተመኘችውን ይቅርታ በቀላሉ ያገኘችው..፡፡ከልጇ ግን ቀላል አልሆነላትም..እናት በመሆን እና ልጅ በመሆን መካከል ያለው ልዩነት ይህ ነው
አሁን ሰኣቱ ከጥዋቱ 2 ሰዓት አካባቢ ነው ፡፡ቤተሰቡ በአንድ ጠረጵዛ ዙሪያ ከበው ቁርስ እየበሉ ነው፡፡አባ ሽፍንፍን፤ ሮዝ ፤እናቶ እና አቤል…ሄለንም ጠረጳዛውን ከባ አብራቸው ባትቀመጥም ሳሎን ውስጥ ግን አለች …የቁርስ ሰሀኗን ለብቻዋ ይዛ ሳሎኑ ጥግ ካለ አንድ ኩርሲ ላይ ቁጭ ብላ በፀጥታ እየበላች ነው..ይሄንን ያደረገችው ለሮዝ አልፈልግሽም የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ ነው..ቁርሱ እንደተጠናቀቀ ልብሷን ቀይራ ወደውጭ ስትወጣ..አያቶ ወደ ማድቤት አቀኑ…በዚህን ጊዜ ሶስቱ ብቻ ቀሩ..ሮዝ አባ ተነስተው ጥለዋት ከመሄዳቸው በፊት በውስጦ ሚተረማመሰውን ነገር መጠየቅ ጀመረች
‹‹አባ››
‹‹አቤት ልጄ››
‹‹እንደው እርሷም ጨከኑብኝ እኮ?››አለቻቸው
‹‹ምነው ልጄ ?ምን አደረግኩሽ..ሳለውቅ ምን አጠፋው?››
‹‹አይ አጥፍተወ አይደለም..ከእናቴ ስላስታረቁኝ እና የሷን ይቅርታ እዳገኝ ስላደረጉኝ ምን ያህል እንደተደሰትኩና የውስጥ ሰላሜም እንደተመለሰልኝ ልነግሮት አልችልም..ሄለን ላይ ግን ዝም አሉኝ››
‹‹አይ ልጄ መች ዝም አልኩ? አሻፈረኝ አለች እኮ…የአባቴን ማንነት ካልነገረቺኝ እናቴ ነች ብዬ ከእሷ ጋር ምነጋገርበት ጉዳይ የለኝም አለችኝ››
‹‹አይ አባ …እርሶም እኮ አልተጫኗትም?››
‹‹እንዴት እጫናታለው ብለሽ ነው…?እሷ ታዳጊ ወጣት እኮ ነች …ወጣቶችን ደግሞ በፀባይ በማግባባት እንጂ በመጫን እና በማስፈራራት የሆነ ነገር እንዲፈጽሙ ማድረግ ደግ አይደለም…አየሽ ልጄ አሁን በግድ ታረቂያት ብዬ በሳገድዳት እርቃችሁ ከልብ የመነጨ ስለማይሆን የእውነት አይሆንም …የእውነት ካልሆነ ደግሞ ዛላቂ አይሆንም ማለት ነው…እንደምታይው ደግሞ ሄለን ለእኔም በጣም የምወዳት ልጄ ነች…በምንም ነገር ልጫናት አልፈልግም..››ሲሉ ብዙም እንደማይረዶት እንቅጩን ነገሯት፡፡
‹‹እና ምን ይሻለኛል?››ጠየቀች አሁንም ተስፋ ባለመቁረጥ
‹‹የሚሻልሽ ጥያቄዋን መመለስ ብቻ ነው…ለማንኛውም አስቢበት አሁን ልለያችሁ ነው››ብለው የመጨረሻ ምክራቸውን በመስጠት ተለይተዋቸው ወደ ጸሎት ክፍላቸው ገብተው በራፍን ከውስጥ ቀረቀሩት…. ሳሎን ውስጥ አቤል እና ሮዝ ብቻ ቀሩ
‹‹አቤል ምን ይሻለኛል?››አለችው ወደ ክፉ ቀን ጓደኛዋ ዞራ….
‹‹እኔም ግራገብቶኛል ..ግን እኮ አባ ያሉት ነገር እውነታቸውን ነው››
‹‹እኔስ እውነታቸውን አይደለም መች አልኩህ….እውነታቸውን ነው እሺ ምን ላድርግ?››እየጮኸች ከመቀመጫዋ ተነሳች እና ሳሎኑን ለቃ ወደ በረንዳው አመራች
…አቤልም መቀመጫውን ለቆ ተከተላት‹‹እሺ ምን ይሻላል?እኔም እኮ የውስጥ ጭንቀትሽን ሳልረዳ ቀርቼ ሳይሆን ቢጨንቀኝ እና ሌላ ዘዴ አልታየህ ቢለኝ ››
‹‹አውቃለው ለእኔ ስትል እየተጨነቅክ እንደሆነ አውቃለው.. ስለጮህኩብህ ይቅርታ››ብላው በረንዳውን ለቃ ደረጃውን ወረደች እና ግቢ ውስጥ ወዳለች ወደ አንድ የዛፍ ጥላ በመሄድ መሬት ሳር ላይ ተቀመጠች ..አቤልም ያደረገችውን ከማድረግ ውጭ ለጊዜው ሌላ ምርጫ ስላልነበረው ተከተላት እና ሄዶ ስሯ ተቀመጠ…ሁለቱም በዝምታ ተውጠው ውስጣቸው ስለሚብላላው ነገር በየግላቸው ማሰላሰል ጀመሩ….በዚህ ቅጽበት ግን ያልጠበቁት ተፍለቅላቂ ሳቅ ከአካባቢው ተሰማ
:
#ክፍል_ሀያ_አራት
:
✍ድርሰት፦በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...አቤል ያገኘውን እድል ባለማመን በጥድፊያ ነበር ወደ ሮዝ የሄደው..ኩምሽሽ ብላ መኪና ውስጥ እንደተቀመጠች ነበር ያገገኛት
‹‹ቆየውብሽ አይደል?››
‹‹የምዕተ ዓመት ያህል ነዋ…በዛ ላይ ሄለን ከግቢው ወጥታ በዛች ቀጭን መንገድ ወደ ጀርባ በኩል ስትሄድ ሳያት ምን ተፈጠረ ብዬ ነፍሴ ልትወጣ ነበር….ስልክህን ስደውልልህ ደግሞ አታነሳም››አለችው ስልችት እንዳላት በሚያሳብቅ እና እንባ በተናነቀው ስሜት
‹‹በይ አሁን እንግባ››
‹‹ወዴት ነው የምንገባው?››
‹‹ወደ ውስጥ ነዋ..አንቺ እኚ ቄስ እግዚያብሄር የባረካቸው ናቸው …ገና አብራርቼ እንኳን ስለመጣንበት ጉዳይ ሳልነግራቸው ነው የተረዱኝ…እንደውም አንቺን እዚህ ውጭ አስቀምጪ ይህን ያህል በመቆየቴ በጣም ነው የገሰጹኝ…እሷን ብቻ ይዘኸት ና …እርቁን ለእኔ ተወው ብለውኛል››
‹‹እውነትህን ነው?›› በጉጉት እና በተስፋ ጠየቀችው
‹‹አዎ ተነሽ እንግባ…ለመሆኑ እማዬ ሰላም ነች››
‹‹ሰላም ናቸው… አሁን ልታያቸው አይደል?››
‹‹ወይ አቤልዬ በጣም ነው የፈራውት… ሽንቴ ሁሉ ሊያመልጠኝ ነው››አለች መኪናውን ለቃ ወደ ውጭ እየወጣች
‹‹አይዞሽ ጠንከር በይ›› ብሎ ስትንገዳገድ ደገፋና የመኪናውን በራፍ ዘግቶ እና ቆልፎ ይዞት ወደ አባ ሽፍንፍን ቤት ተጓዘ ..ልክ እቤት ደርሰው የሳሎንን በራፍ አልፋው ወደ ውስጥ እደገቡ እናትዬው በተቀመጡበት ቀና ብለው ሲያዩት እና ልጃቸው ሮዝ መሆኖን ሲያውቁ‹‹ወይኔ ጉዴ!!!›› ብለው ጩኹ….ጩኸታቸው ሮዝን ብቻ ሳይሆን ሌሎችንም አስደነገጠ.
‹‹ግቡ.. ግቡ ››በማለት አባ አቤል እና ሮዝ ተረጋግተው ወደውስጥ እንዲገቡ አበረታቶቸው…
‹‹እማዬ›› አለች ሮዝ ወደውስጥ በዝግታ እየመጣች
‹‹እማዬ አትበይኝ አንቺ ጉድ!! ››አሏት በተቀመጡበት ደንግጠው አፋቸውን በእጃቸው እንደያዙ
‹‹እማ ባክሽ ናፍቀሺኛል …በጣም ናፍቀሺኛል..››አለቻቸው…እናትዬው ፀጥ እንዳሉ ነው… እንባቸው በጉንጫቸው ላይ ተንኳለለ.. ሮዝ ተንደርድራ ወደተቀመጡበት ሄደችና እግራቸው ላይ ተዘረገፈች
‹‹እባክሽ እማ..እኔስ ማን አለኝ? ይቅር በይኝ ..እንደድሮሽ እንደልጅነቴ ተቆጥተሺኝ ና ገርፈሺኝ መልሰሽ አባበብይኝ…እማ ጠረንሽ ናፍቆኛል..እማ ትንፋሽሽ ርቦኛል…››አባ ሽፍንፍን በተቀመጡበት አቤል እንደቆመ ሁኔታውን እየተከታተሉ ነው፡፡
እናትዬው ዝም እንዳሉ ነው….. የሚያደርጉት ግራ ገብቷቸዋል…በዚህ ጊዜ አባ ሽፍንፍን መስቀላቸውን ከኪሳቸውን አወጡና ቆሙ ‹‹እንግዲህ ሰው ሆኖ ለዛውም ልጅ ሆኖ የማያጠፋ የለም…በቃ ይቅር በሏት ››ሲሉ መሸምገላቸውን ጀመሩ
‹‹አባ እርሶ እኮ ስለእሷ ሁሉንም አያውቁም››
‹‹ግድ የለም ሁሉንም ማወቅ አያስፈልገኝም..ግን እርግጠኛ ነኝ ከይቅርታ በላይ የሆነ በደል የለም..በዛ ላይ እናት በልጆ ላይ አትጨክንም..››
‹‹እርሱማ እንዴት ብዬ ጨክናለው?››
‹‹እግዜር ያክብሮት ..እመብርሀን እድሜ ትስጦት›› አባ መረቁ
‹‹በይ ተነሽ ››አሏት እናቷ ጭንቅላቷን እያሻሹ…
‹‹ይቅር አልሺኝ እማ..በቃ ታረቅን?››ባለማን እና በመነፍረቅ ጠየቀች
‹‹ተነሺ አልኩሽ እኮ…››ብለው ተከሻውና አነሱ እና ቀና እንድትል አደረጐትና በስስት እና በናፍቆት ጉንጯን ለመሳም ወደ እሷ በተሳቡበት ደቂቃ ሄለን ለፒያኖ ልምምድ የቀረውን ኩማደሩን ጥበቃ አሰልችቶት በመመለስ የሳሎኑን በራፍ ከፍታ ገባች..ፊት ለፊቷ የሚከወነውን ነገር ስታይ በድንዛዜ ሀውልት ሆና ነው የቋመችው፡፡
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ሮዝ እና አቤል ሻሸመኔ አባ ሽፍንፍን ቤት ከከተሙ ሶስት ቀን አልፎቸዋል…በእነዚህ ቀናቶች ውስጥ የሮዝ ስሜት ግምሽ ደስታ ግማሽ ሀዘን….ግማሽ ሳቅ ግማሽ ለቅሶ ሁኖ ነው የሰነበተው፡፡ይህ የሆነበት ምክንያት ባላሰበችው ፍጥነት ከእናቷ ይቅርታን አግኝታ የውስጥ ሰላም ብታገኝም…ልጇ ሄለን ግን እስከአሁን አሻፈረኝ እንዳለቻት ነው፡፡በዚህ ክስተት አንድ እውነት ገብቷታል…እናትነት እና ልጅነት መካከል ያለውን ልዩነት…እናትነት የፍቅር ጥግ መግለጫ ነው..እናትነት የይቅር ባይነት የመጨረሻ ማሳያ ነው…ለዚህ ነው ከእናቷ የተመኘችውን ይቅርታ በቀላሉ ያገኘችው..፡፡ከልጇ ግን ቀላል አልሆነላትም..እናት በመሆን እና ልጅ በመሆን መካከል ያለው ልዩነት ይህ ነው
አሁን ሰኣቱ ከጥዋቱ 2 ሰዓት አካባቢ ነው ፡፡ቤተሰቡ በአንድ ጠረጵዛ ዙሪያ ከበው ቁርስ እየበሉ ነው፡፡አባ ሽፍንፍን፤ ሮዝ ፤እናቶ እና አቤል…ሄለንም ጠረጳዛውን ከባ አብራቸው ባትቀመጥም ሳሎን ውስጥ ግን አለች …የቁርስ ሰሀኗን ለብቻዋ ይዛ ሳሎኑ ጥግ ካለ አንድ ኩርሲ ላይ ቁጭ ብላ በፀጥታ እየበላች ነው..ይሄንን ያደረገችው ለሮዝ አልፈልግሽም የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ ነው..ቁርሱ እንደተጠናቀቀ ልብሷን ቀይራ ወደውጭ ስትወጣ..አያቶ ወደ ማድቤት አቀኑ…በዚህን ጊዜ ሶስቱ ብቻ ቀሩ..ሮዝ አባ ተነስተው ጥለዋት ከመሄዳቸው በፊት በውስጦ ሚተረማመሰውን ነገር መጠየቅ ጀመረች
‹‹አባ››
‹‹አቤት ልጄ››
‹‹እንደው እርሷም ጨከኑብኝ እኮ?››አለቻቸው
‹‹ምነው ልጄ ?ምን አደረግኩሽ..ሳለውቅ ምን አጠፋው?››
‹‹አይ አጥፍተወ አይደለም..ከእናቴ ስላስታረቁኝ እና የሷን ይቅርታ እዳገኝ ስላደረጉኝ ምን ያህል እንደተደሰትኩና የውስጥ ሰላሜም እንደተመለሰልኝ ልነግሮት አልችልም..ሄለን ላይ ግን ዝም አሉኝ››
‹‹አይ ልጄ መች ዝም አልኩ? አሻፈረኝ አለች እኮ…የአባቴን ማንነት ካልነገረቺኝ እናቴ ነች ብዬ ከእሷ ጋር ምነጋገርበት ጉዳይ የለኝም አለችኝ››
‹‹አይ አባ …እርሶም እኮ አልተጫኗትም?››
‹‹እንዴት እጫናታለው ብለሽ ነው…?እሷ ታዳጊ ወጣት እኮ ነች …ወጣቶችን ደግሞ በፀባይ በማግባባት እንጂ በመጫን እና በማስፈራራት የሆነ ነገር እንዲፈጽሙ ማድረግ ደግ አይደለም…አየሽ ልጄ አሁን በግድ ታረቂያት ብዬ በሳገድዳት እርቃችሁ ከልብ የመነጨ ስለማይሆን የእውነት አይሆንም …የእውነት ካልሆነ ደግሞ ዛላቂ አይሆንም ማለት ነው…እንደምታይው ደግሞ ሄለን ለእኔም በጣም የምወዳት ልጄ ነች…በምንም ነገር ልጫናት አልፈልግም..››ሲሉ ብዙም እንደማይረዶት እንቅጩን ነገሯት፡፡
‹‹እና ምን ይሻለኛል?››ጠየቀች አሁንም ተስፋ ባለመቁረጥ
‹‹የሚሻልሽ ጥያቄዋን መመለስ ብቻ ነው…ለማንኛውም አስቢበት አሁን ልለያችሁ ነው››ብለው የመጨረሻ ምክራቸውን በመስጠት ተለይተዋቸው ወደ ጸሎት ክፍላቸው ገብተው በራፍን ከውስጥ ቀረቀሩት…. ሳሎን ውስጥ አቤል እና ሮዝ ብቻ ቀሩ
‹‹አቤል ምን ይሻለኛል?››አለችው ወደ ክፉ ቀን ጓደኛዋ ዞራ….
‹‹እኔም ግራገብቶኛል ..ግን እኮ አባ ያሉት ነገር እውነታቸውን ነው››
‹‹እኔስ እውነታቸውን አይደለም መች አልኩህ….እውነታቸውን ነው እሺ ምን ላድርግ?››እየጮኸች ከመቀመጫዋ ተነሳች እና ሳሎኑን ለቃ ወደ በረንዳው አመራች
…አቤልም መቀመጫውን ለቆ ተከተላት‹‹እሺ ምን ይሻላል?እኔም እኮ የውስጥ ጭንቀትሽን ሳልረዳ ቀርቼ ሳይሆን ቢጨንቀኝ እና ሌላ ዘዴ አልታየህ ቢለኝ ››
‹‹አውቃለው ለእኔ ስትል እየተጨነቅክ እንደሆነ አውቃለው.. ስለጮህኩብህ ይቅርታ››ብላው በረንዳውን ለቃ ደረጃውን ወረደች እና ግቢ ውስጥ ወዳለች ወደ አንድ የዛፍ ጥላ በመሄድ መሬት ሳር ላይ ተቀመጠች ..አቤልም ያደረገችውን ከማድረግ ውጭ ለጊዜው ሌላ ምርጫ ስላልነበረው ተከተላት እና ሄዶ ስሯ ተቀመጠ…ሁለቱም በዝምታ ተውጠው ውስጣቸው ስለሚብላላው ነገር በየግላቸው ማሰላሰል ጀመሩ….በዚህ ቅጽበት ግን ያልጠበቁት ተፍለቅላቂ ሳቅ ከአካባቢው ተሰማ
👍1
የሄለን ነበር..፡፡ዞር ዞር ብለው ፈለጓት… ግቢው ውስጥ አትታይም…ግራ ገባቸው..፡፡
ወዲያው ግን ሮዝ የልጇ ድምጽ የተሰማበትን አቅጣጫ አወቀች...ከፎቅ ላይ ነው፡፡ፎቅ በረንዳ ላይ ፊቷን ወደእነሱ አቅጣጫ አዙራ ቀልቧን ግን ከፊት ለፊቷ ያለው ሰው ላይ ብቻ አኑራ ትታያለች …ጀርባውን ለእነሱ የሰጠ ሌላ ሰው አብሯት አለ …ፒያኖ የሚያስጠናት ሰው እንደሆነ ወዲያው ነው ያወቀችው…ስሜቷ ተነቃቃ..እዚህ ቤት እግሯ ከረገጠበት ቀን አንስቶ ይሄንን ሰው በአካል ልታየው ብዙ ቀን ሞክራ ነበር ..ዛሬ ተሳካላት፡፡ፊቱን ወደ እኛ ቢያዞር..ብላ በተመኘችበት ቅጽበት ሰውዬው ከመቀመጫው ተነሳና ቋመ …ወደቤት ሊገባ መስሏት ነበር…. ግን ፊቱን ወደ እነሱ አዞረ እና በረንዳውን ተደግፎ ከሄለን ጋር ማውራቱን ቀጠለ..በዚህን ጊዜ ሮዝ አይኖን ማመን አቃታት…አቅለሸለሻት… አጥወለወላት‹‹..እንዴ ..!!እነዴ…!! የፈጣሪ ያለህ!!!››
‹‹ምን ሆንሽ…?ምን ተፈጠረ?›› ግራ በመጋባት ዙሪያዋን እየተሸከረከረ ለፈለፈ… አቤል
‹‹እሱ ነው …እሱ እራሱ ነው››እጇን ወደ መሀሪ ቀሰረች..መሀሪ እጁን አውለበለበላት እና ሄለንን ከመቀመጫዋ አስነቶ እየጎተተ ወደ ውስጥ ይዞት ገባ….ሄለን ቀልቧ ከጫወታዋ እና ከኩማንደሩ ላይ ብቻ ስለነበረ እታች ምድር የሚገኙትን አቤልን እና እናቷን አላየቻቸውም…..
ግራ የተጋባው አቤል‹‹እሱ ማን ነው ?ምን ነካሽ?››
‹‹ተወኝ አቤልዬ….በጣም አደጋ ላይ ነኝ …አክትሞልኛል››
‹‹ ኸረ ምን ሆንሽ? አስጨነቅሺኝ እኮ!!››
‹‹ሄለንን ፒያኖ የሚያሰለጥናት…››
‹‹እ..ምን ሆነ?››
‹‹የዲላው እጮኛዬ ነው››
‹‹እጮኛዬ››በሰማው ቃላት እርግጠኛ መሆን አልቻለወም
‹‹አዎ እርግጠኛ ነኝ በእሷ በኩል ሊበቀለኝ ነው..በቃ ሊያወድመኝ ነው››በለቅሶ ታጅባ ለፈለፈች
‹‹ኸረ ተረጋጊ››
‹‹ምኑን ተረጋጋውት… በአስቸኳይ የሆነ ነገር ማድረግ አለብን..አባን አሁኑኑ ማግኘት አለብኝ››ከተቀመጠችበት ተነሳችና ወደቤት አመራች
‹‹እንዴ እሳቸው እኮ ፀሎት ላይ ናቸው››እያለ ከኃላዋ ተከተላት
‹‹ቢሆንም ላገኛቸው የግድ ነው››እያለች ወደ እናትዬው ጋር ሄደች ኩሽና ..አቤል ሳሎን ቀረ
‹‹እማ ..እማዬ››
‹‹አቤት ምነው ጥድፍ ጥድፍ አልሽ?..ደግሞ ለቅሶው ምንድነው?››
‹‹አባን ፈልጌ ነበር?››
‹‹እንዴ አሁን አብራሻቸው አልነበርሽ እንዴ?››
‹‹ነበሩ ግን ወደ ጸሎት ቤታቸው ገብተዋል››
‹‹እንግዲያውስ እስኪወጡ መጠበቅ ነዋ››
‹‹እማ አልችልም አሁኑኑ ነው የምፈልጋቸው››
‹‹ማይቻለውን..እሳቸው እዚህ ቤት ሲያመጡን የነገሩን ብቸኛ ማስጠንቀቂያ ቢኖር እሷቸው ወደ ፀሎት ቤታቸው ከገቡ ቡኃላ እቤቱ በእሳት ቢቀጣጠል እንኳን በራቸውን እንዳናንኳኳ ነው..ስለዚህ በምንም አይነት ምክንያት ከጸሎታቸው ልንረብሻቸው አንችልም››
‹‹እሺ መች ነው የሚጨርሱት?››
‹‹እኔ ምን አውቄ ልጄ ..ዛሬም…ነገም… ተነገ ወዲያም ሊጨርሱ ይችላሉ››
‹‹ኦ አምላክ..ታዲያ ምን ይሻላል?››
‹‹ምን ተፈጥሮ ነው ይሄ ሁሉ ጉድ እና ጥድፊያ?››
‹‹እማ ሄለን አደጋ ላይ ነች››
‹‹የምን አደጋ ?ልጄ ምን ሆነች..?››ድንጋጤው በእጥፍ ተባዝቶ በእሷቸው ላይ ተጋባ
‹‹ይሄ ፒያኖ የሚያሰለጥናት ሰውዬ…››
‹‹ኩማደሩ. ምን ሆነ?››
‹‹ምን ይሆናል …ዲላ ነበር የሚኖረው››
‹‹አዎ ሰምቼያለው..ታዲያ ምን ችግር አለው?››
‹‹እኔ አውቀው ነበር››
‹‹እወቂዋ… ታዲያ ማወቅ መልካም ይሆናል እንጂ ምን ክፋት ሊኖረው?››
‹‹እማ አልገባሽም ጥለኞች ነበርን…በጣም ነው የሚጠላኝ..ሊገድለኝ ሁሉ ይፈልጋል›››
‹‹አይ አንቺ ልጅ… በቃ ያንቺ መዘዝ ዘላለም ማለቂያ የለውም ..?ይሄውልሽ ሮዝ በአንቺ የተነሳ ልጄ ከእጣቷ ላይ አንዲት ስንጣሪ ጠፍሯ ያለፍቃዷ ተቆርጣ ብትወድቅባት በቃ… የእኔ እና የአንቺ ነገር ዳግም ላይቀጠል አከተመለት ማለት ነው›› በማለት ጭራሽ በጭንቀት ላይ ጭንቀት ጨመሩባት…ተስፈንጥራ ከማድቤት ወጥታ ሄደች… ሳሎኑን አለፈችና ወደ ውጭ ወጣች‹‹የት ልትሄጂ ነው›› ሳሎን የነበረው አቤል ተከተላት
‹‹አቤል ይሄን ሰውዬ ላነጋግረው እፈልጋለው..እዚሁ ጠብቀኝ››
‹‹ኸረ ሮዝ ተረጋጊና በሰከነ አዕምሮ ነገሮችን አስቢያቸው..ምን አልባት ነገሮች በአጋጣሚ ተገጣጥመው እንጂ እንቺ እንደምትይው የታሰበባቸው ላይሆን ይችላሉ››
ልትሰማው አልፈለገችም..እንደ አመለኛ በቅሎ እየሰገረች ግቢውን ለቃ ወጣች…እንዴት እንደዞረች… እንዴት ግቢውን እንደከፈተችና የፎቁን ደረጃ እንዴት ተንደርድራ እንደወጣች ለራሷም አታውቅም..በራፍንም ሳታንኳኳ በራፍን በርግዳ ከፈተች..ሄለን ፒያኖው ፊት ለፊት ተቀምጣ ጣቶቾን ከወዲህ ወዲያ የሙዚቃ መሳሪያውን በማርመስመስ ሙዚቃ እየተጫወተች ነው፡፡ኩማደሩ ከሄለን ኃላ ቆሞ እጆቹን ተከሻዋ ላይ ጣል አድርጐ በአድናቆት እየተመለከታት ነበር..በራፍ ድንገት ሲከፈት ተገርሞ ዞር አለ፡፡
..የእንግዳዋን ማንነት ሲያውቅ ፈገግ አለ…አዎ እንዳየችው እንደምትመጣ እርግጠኛ ነበር
‹‹አቤት ምን ነበር?››አለት ሄለን እሷን ያላት በመስሎት ግራ ገብቶት ቀና ስትል አይኗ የተገተረችው ሮዝ ላይ አረፈ….ፒያኖዋን መጫወቷን አቆመች
‹‹ሄለን አንዴ ቤቱን ትለቂልን እና ወደቤት ትሄጂ››
‹‹አልገባኝም…እንደምታይው ስራ ላይ ነው ያለነው..ጉዳይ ካለሽ ለምን አንቺ ሌላ ጊዜ አትመለሺም››አላገጠባት
‹‹ሰይጣኔን አታምጣው..አንቺ ውጪ ብዬሻላ ውጪ ››ተንደርድራ ትከሻዋን ያዘችና ከተቀመጠችበት አንጠልጥላ አነሳቻት
‹‹እንዴ ልቀቂኝ እንጂ ..አብደሻል እንዴ?››
‹‹አዎ አብጄያለው..አሁን ልቀቂና ውጪ ብዬሻለው››
ኩማንደር ውስጡ በደስታ ረሰረሰች ባለፈው አግኝቷት አንዱን ጠላቱን በበቂ መንገድ ተበቅላለታለች የሷ ግን ገና ነው ይህቺን ቀንም በጉጉትቶ ነበር ሲጠብቅ የነበረው… ‹‹የእኔ ቆንጆ ግድየለሽም እስቲ ውጪላት ..ዛሬ ስራ ስለማልሄድ እንደጨረስን እደውልልሽ እና ካቆምንበት እንቀጥላለን››አለት
‹‹ምን አይነት ጣጣ ነው? ለምንድነው የምትከታተይኝ..?ለምንድነው የማትተይኝ…? በቃ አላውቅሽም አታውቂኝም››ብላ እየተማናጨቀች እቤቱን ለሁለቱ ተፋላላጊዎች ለቃ ወደ ቤቷ ተመልሳ ሄደች..
አሁን ሁለቱ ሰዎች እንደተፋጠጡ ናቸው ….. ኩማንደር መቀመጨ ይዞ ቁጭ አለ‹‹እሺ ምንድነበር ጉዳይሽ ወይዘሪት ሮዝ?››
‹‹ምን እየሰራህ ነው?››
‹‹አልገባኝም..ምንስ ብሰራ ሚስቴ አይደለሽ ሀለቃዬ… ምን አስጨነቀሽ?››
‹‹አታሹፍ… ከዚ በፊትም ነግሬካለው እኔን እንደፈለግክ ማድረግ ትችላለህ..ከፈለግክ ስጋዬን ዘልዝለህ ለውሻ ልትሰጠኝ ትችላለህ.. ልጄን ግን ተዋት ብዙ መከራ ያየውባት..ህይወቴ የተመሰቃቀለባት የመከራይ ውጤት ነች››
‹‹ምን እንደምትይ አልገባኝም?››
‹‹በደንብ ይገባሀል…ከልጄ ጋር ያለህን ግንኙነት አቁም ነው እያልኩህ ያለውት..››
‹‹እውነት እሱን እንኳን አልችልም..እሷን ተዋት ከምትይኝ ህይወትህን አሳልፈህ ስጠኝ ብትይኝ ይቀለኛል››
‹‹እንዴ!!! ምን ማለት ነው?››
‹‹ቀሪ ህይወቴን ከሄልዬ ተለይቼ መኖር አልችልም እያልኩሽ ነው››
‹‹እየቀለድ እንደሆነ እርግጠኛ ነኝ…እኔ እስከማውቅህ ድረስ ብትወልዳት ልታደርሳት ከምትችላት ልጅ ጋር ሌላ ግንኙነት ለመጀመር የሚያስችል የዘቀጠ ስብዕና ያለህ አይመስለኝም››
‹‹እሱማ ድሮ ነበር… አሁን እኮ በጣም ተቀይሬያለው፡፡ አንቺና ውሽማሽ ኩማንደር ደረሰ ብዙ ብዙ ነገር አስተምራችሁኛል…ስለዚህ እስከ አሁን ያልኩሽን በፍፁም የውሸቴን አይደለም..በጣም አፍቅሬያታለው…እሷም ያፈቀረችኝ ይመስለኛል..ይሄን ማረጋገጥ ከፈለግሽ ከእሷም
ወዲያው ግን ሮዝ የልጇ ድምጽ የተሰማበትን አቅጣጫ አወቀች...ከፎቅ ላይ ነው፡፡ፎቅ በረንዳ ላይ ፊቷን ወደእነሱ አቅጣጫ አዙራ ቀልቧን ግን ከፊት ለፊቷ ያለው ሰው ላይ ብቻ አኑራ ትታያለች …ጀርባውን ለእነሱ የሰጠ ሌላ ሰው አብሯት አለ …ፒያኖ የሚያስጠናት ሰው እንደሆነ ወዲያው ነው ያወቀችው…ስሜቷ ተነቃቃ..እዚህ ቤት እግሯ ከረገጠበት ቀን አንስቶ ይሄንን ሰው በአካል ልታየው ብዙ ቀን ሞክራ ነበር ..ዛሬ ተሳካላት፡፡ፊቱን ወደ እኛ ቢያዞር..ብላ በተመኘችበት ቅጽበት ሰውዬው ከመቀመጫው ተነሳና ቋመ …ወደቤት ሊገባ መስሏት ነበር…. ግን ፊቱን ወደ እነሱ አዞረ እና በረንዳውን ተደግፎ ከሄለን ጋር ማውራቱን ቀጠለ..በዚህን ጊዜ ሮዝ አይኖን ማመን አቃታት…አቅለሸለሻት… አጥወለወላት‹‹..እንዴ ..!!እነዴ…!! የፈጣሪ ያለህ!!!››
‹‹ምን ሆንሽ…?ምን ተፈጠረ?›› ግራ በመጋባት ዙሪያዋን እየተሸከረከረ ለፈለፈ… አቤል
‹‹እሱ ነው …እሱ እራሱ ነው››እጇን ወደ መሀሪ ቀሰረች..መሀሪ እጁን አውለበለበላት እና ሄለንን ከመቀመጫዋ አስነቶ እየጎተተ ወደ ውስጥ ይዞት ገባ….ሄለን ቀልቧ ከጫወታዋ እና ከኩማንደሩ ላይ ብቻ ስለነበረ እታች ምድር የሚገኙትን አቤልን እና እናቷን አላየቻቸውም…..
ግራ የተጋባው አቤል‹‹እሱ ማን ነው ?ምን ነካሽ?››
‹‹ተወኝ አቤልዬ….በጣም አደጋ ላይ ነኝ …አክትሞልኛል››
‹‹ ኸረ ምን ሆንሽ? አስጨነቅሺኝ እኮ!!››
‹‹ሄለንን ፒያኖ የሚያሰለጥናት…››
‹‹እ..ምን ሆነ?››
‹‹የዲላው እጮኛዬ ነው››
‹‹እጮኛዬ››በሰማው ቃላት እርግጠኛ መሆን አልቻለወም
‹‹አዎ እርግጠኛ ነኝ በእሷ በኩል ሊበቀለኝ ነው..በቃ ሊያወድመኝ ነው››በለቅሶ ታጅባ ለፈለፈች
‹‹ኸረ ተረጋጊ››
‹‹ምኑን ተረጋጋውት… በአስቸኳይ የሆነ ነገር ማድረግ አለብን..አባን አሁኑኑ ማግኘት አለብኝ››ከተቀመጠችበት ተነሳችና ወደቤት አመራች
‹‹እንዴ እሳቸው እኮ ፀሎት ላይ ናቸው››እያለ ከኃላዋ ተከተላት
‹‹ቢሆንም ላገኛቸው የግድ ነው››እያለች ወደ እናትዬው ጋር ሄደች ኩሽና ..አቤል ሳሎን ቀረ
‹‹እማ ..እማዬ››
‹‹አቤት ምነው ጥድፍ ጥድፍ አልሽ?..ደግሞ ለቅሶው ምንድነው?››
‹‹አባን ፈልጌ ነበር?››
‹‹እንዴ አሁን አብራሻቸው አልነበርሽ እንዴ?››
‹‹ነበሩ ግን ወደ ጸሎት ቤታቸው ገብተዋል››
‹‹እንግዲያውስ እስኪወጡ መጠበቅ ነዋ››
‹‹እማ አልችልም አሁኑኑ ነው የምፈልጋቸው››
‹‹ማይቻለውን..እሳቸው እዚህ ቤት ሲያመጡን የነገሩን ብቸኛ ማስጠንቀቂያ ቢኖር እሷቸው ወደ ፀሎት ቤታቸው ከገቡ ቡኃላ እቤቱ በእሳት ቢቀጣጠል እንኳን በራቸውን እንዳናንኳኳ ነው..ስለዚህ በምንም አይነት ምክንያት ከጸሎታቸው ልንረብሻቸው አንችልም››
‹‹እሺ መች ነው የሚጨርሱት?››
‹‹እኔ ምን አውቄ ልጄ ..ዛሬም…ነገም… ተነገ ወዲያም ሊጨርሱ ይችላሉ››
‹‹ኦ አምላክ..ታዲያ ምን ይሻላል?››
‹‹ምን ተፈጥሮ ነው ይሄ ሁሉ ጉድ እና ጥድፊያ?››
‹‹እማ ሄለን አደጋ ላይ ነች››
‹‹የምን አደጋ ?ልጄ ምን ሆነች..?››ድንጋጤው በእጥፍ ተባዝቶ በእሷቸው ላይ ተጋባ
‹‹ይሄ ፒያኖ የሚያሰለጥናት ሰውዬ…››
‹‹ኩማደሩ. ምን ሆነ?››
‹‹ምን ይሆናል …ዲላ ነበር የሚኖረው››
‹‹አዎ ሰምቼያለው..ታዲያ ምን ችግር አለው?››
‹‹እኔ አውቀው ነበር››
‹‹እወቂዋ… ታዲያ ማወቅ መልካም ይሆናል እንጂ ምን ክፋት ሊኖረው?››
‹‹እማ አልገባሽም ጥለኞች ነበርን…በጣም ነው የሚጠላኝ..ሊገድለኝ ሁሉ ይፈልጋል›››
‹‹አይ አንቺ ልጅ… በቃ ያንቺ መዘዝ ዘላለም ማለቂያ የለውም ..?ይሄውልሽ ሮዝ በአንቺ የተነሳ ልጄ ከእጣቷ ላይ አንዲት ስንጣሪ ጠፍሯ ያለፍቃዷ ተቆርጣ ብትወድቅባት በቃ… የእኔ እና የአንቺ ነገር ዳግም ላይቀጠል አከተመለት ማለት ነው›› በማለት ጭራሽ በጭንቀት ላይ ጭንቀት ጨመሩባት…ተስፈንጥራ ከማድቤት ወጥታ ሄደች… ሳሎኑን አለፈችና ወደ ውጭ ወጣች‹‹የት ልትሄጂ ነው›› ሳሎን የነበረው አቤል ተከተላት
‹‹አቤል ይሄን ሰውዬ ላነጋግረው እፈልጋለው..እዚሁ ጠብቀኝ››
‹‹ኸረ ሮዝ ተረጋጊና በሰከነ አዕምሮ ነገሮችን አስቢያቸው..ምን አልባት ነገሮች በአጋጣሚ ተገጣጥመው እንጂ እንቺ እንደምትይው የታሰበባቸው ላይሆን ይችላሉ››
ልትሰማው አልፈለገችም..እንደ አመለኛ በቅሎ እየሰገረች ግቢውን ለቃ ወጣች…እንዴት እንደዞረች… እንዴት ግቢውን እንደከፈተችና የፎቁን ደረጃ እንዴት ተንደርድራ እንደወጣች ለራሷም አታውቅም..በራፍንም ሳታንኳኳ በራፍን በርግዳ ከፈተች..ሄለን ፒያኖው ፊት ለፊት ተቀምጣ ጣቶቾን ከወዲህ ወዲያ የሙዚቃ መሳሪያውን በማርመስመስ ሙዚቃ እየተጫወተች ነው፡፡ኩማደሩ ከሄለን ኃላ ቆሞ እጆቹን ተከሻዋ ላይ ጣል አድርጐ በአድናቆት እየተመለከታት ነበር..በራፍ ድንገት ሲከፈት ተገርሞ ዞር አለ፡፡
..የእንግዳዋን ማንነት ሲያውቅ ፈገግ አለ…አዎ እንዳየችው እንደምትመጣ እርግጠኛ ነበር
‹‹አቤት ምን ነበር?››አለት ሄለን እሷን ያላት በመስሎት ግራ ገብቶት ቀና ስትል አይኗ የተገተረችው ሮዝ ላይ አረፈ….ፒያኖዋን መጫወቷን አቆመች
‹‹ሄለን አንዴ ቤቱን ትለቂልን እና ወደቤት ትሄጂ››
‹‹አልገባኝም…እንደምታይው ስራ ላይ ነው ያለነው..ጉዳይ ካለሽ ለምን አንቺ ሌላ ጊዜ አትመለሺም››አላገጠባት
‹‹ሰይጣኔን አታምጣው..አንቺ ውጪ ብዬሻላ ውጪ ››ተንደርድራ ትከሻዋን ያዘችና ከተቀመጠችበት አንጠልጥላ አነሳቻት
‹‹እንዴ ልቀቂኝ እንጂ ..አብደሻል እንዴ?››
‹‹አዎ አብጄያለው..አሁን ልቀቂና ውጪ ብዬሻለው››
ኩማንደር ውስጡ በደስታ ረሰረሰች ባለፈው አግኝቷት አንዱን ጠላቱን በበቂ መንገድ ተበቅላለታለች የሷ ግን ገና ነው ይህቺን ቀንም በጉጉትቶ ነበር ሲጠብቅ የነበረው… ‹‹የእኔ ቆንጆ ግድየለሽም እስቲ ውጪላት ..ዛሬ ስራ ስለማልሄድ እንደጨረስን እደውልልሽ እና ካቆምንበት እንቀጥላለን››አለት
‹‹ምን አይነት ጣጣ ነው? ለምንድነው የምትከታተይኝ..?ለምንድነው የማትተይኝ…? በቃ አላውቅሽም አታውቂኝም››ብላ እየተማናጨቀች እቤቱን ለሁለቱ ተፋላላጊዎች ለቃ ወደ ቤቷ ተመልሳ ሄደች..
አሁን ሁለቱ ሰዎች እንደተፋጠጡ ናቸው ….. ኩማንደር መቀመጨ ይዞ ቁጭ አለ‹‹እሺ ምንድነበር ጉዳይሽ ወይዘሪት ሮዝ?››
‹‹ምን እየሰራህ ነው?››
‹‹አልገባኝም..ምንስ ብሰራ ሚስቴ አይደለሽ ሀለቃዬ… ምን አስጨነቀሽ?››
‹‹አታሹፍ… ከዚ በፊትም ነግሬካለው እኔን እንደፈለግክ ማድረግ ትችላለህ..ከፈለግክ ስጋዬን ዘልዝለህ ለውሻ ልትሰጠኝ ትችላለህ.. ልጄን ግን ተዋት ብዙ መከራ ያየውባት..ህይወቴ የተመሰቃቀለባት የመከራይ ውጤት ነች››
‹‹ምን እንደምትይ አልገባኝም?››
‹‹በደንብ ይገባሀል…ከልጄ ጋር ያለህን ግንኙነት አቁም ነው እያልኩህ ያለውት..››
‹‹እውነት እሱን እንኳን አልችልም..እሷን ተዋት ከምትይኝ ህይወትህን አሳልፈህ ስጠኝ ብትይኝ ይቀለኛል››
‹‹እንዴ!!! ምን ማለት ነው?››
‹‹ቀሪ ህይወቴን ከሄልዬ ተለይቼ መኖር አልችልም እያልኩሽ ነው››
‹‹እየቀለድ እንደሆነ እርግጠኛ ነኝ…እኔ እስከማውቅህ ድረስ ብትወልዳት ልታደርሳት ከምትችላት ልጅ ጋር ሌላ ግንኙነት ለመጀመር የሚያስችል የዘቀጠ ስብዕና ያለህ አይመስለኝም››
‹‹እሱማ ድሮ ነበር… አሁን እኮ በጣም ተቀይሬያለው፡፡ አንቺና ውሽማሽ ኩማንደር ደረሰ ብዙ ብዙ ነገር አስተምራችሁኛል…ስለዚህ እስከ አሁን ያልኩሽን በፍፁም የውሸቴን አይደለም..በጣም አፍቅሬያታለው…እሷም ያፈቀረችኝ ይመስለኛል..ይሄን ማረጋገጥ ከፈለግሽ ከእሷም
👍1
ጠይቀሽ መረዳት ትችያለሽ…በመካከላችን ላለው ዕድሜ ልዬነት ብዙ አትጨነቂ..ፍቅር በሁለት ተጣማሪዎች መካከል የሚገኙ ማንኛውንም ልዩነቶች የሚያጠፋበት የራሱ የሆነ ላጲስ አለው››
‹‹አንተ አውሬ …አንተ ጨካኝ..››ተንደርድራ ሄዳ ተከመረችበት ፤ ጠፈጠፈችው ፤በተቀመጠበት እራሱን ከመከላከል በስተቀር ምንም አላደረገም…ምክንያቱም እሷ የብስጭት እና የንዴት ጣሪያ ላይ ስትደርስ እሱ ደግሞ ደስታ እያጥለቀለቀው ነበር
‹‹ኸረ በፈጠረህ …እሺ በምታምነው አምላክ ተለመነኝ….. ልጄን ተውልኝ››
‹‹እንዲህ በቀላሉማ እንዴት ይሆናል…?››
‹‹እሺ እንድትተዋት ምን ላድርግ ..እራሴን ላጥፋልህ..ምን ላድርግ ንገረኝ?››
ከባለፈው ከሰጠሁሽ
ሁለት ትእዛዞች አንዱን አልፈፀምሽም ይሄ ደሞ ያሰብኩትን እንዳረግ አስገድዶኛል
‹‹በፈጠረህ አስብበት..ለልጄ በቃ የመጨረሻዋን እስትንፋሴንም ቢሆን እሰጣለው››
‹‹አይ እንድትሞቼ እንኳን አልፈልግም
አንድ እድል እሰጥሻለሁ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሄለን አባት ማን እንደሆነ በራስሽ ድምፅ ቀድተሽ በእጄ እንድሰጪኝ ካለበለዝያ እየፈራሽው ያለው ነገር ሁሉ ይሆናል ይሄንን ማድረግ ከቻልሽ ግን ከልጅሽ ጋር ያለው ነገር አያሳስብሽ
‹‹አሺ እግዜር ይስጥልኝ››ብላ ቅዝቅዝ እንዳለች…. በእንባ እንደታጠበች..በስጋት እንደተወጠረች….እቤቱን ለቃ ወጥታ ሄደች
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
‹‹አንተ አውሬ …አንተ ጨካኝ..››ተንደርድራ ሄዳ ተከመረችበት ፤ ጠፈጠፈችው ፤በተቀመጠበት እራሱን ከመከላከል በስተቀር ምንም አላደረገም…ምክንያቱም እሷ የብስጭት እና የንዴት ጣሪያ ላይ ስትደርስ እሱ ደግሞ ደስታ እያጥለቀለቀው ነበር
‹‹ኸረ በፈጠረህ …እሺ በምታምነው አምላክ ተለመነኝ….. ልጄን ተውልኝ››
‹‹እንዲህ በቀላሉማ እንዴት ይሆናል…?››
‹‹እሺ እንድትተዋት ምን ላድርግ ..እራሴን ላጥፋልህ..ምን ላድርግ ንገረኝ?››
ከባለፈው ከሰጠሁሽ
ሁለት ትእዛዞች አንዱን አልፈፀምሽም ይሄ ደሞ ያሰብኩትን እንዳረግ አስገድዶኛል
‹‹በፈጠረህ አስብበት..ለልጄ በቃ የመጨረሻዋን እስትንፋሴንም ቢሆን እሰጣለው››
‹‹አይ እንድትሞቼ እንኳን አልፈልግም
አንድ እድል እሰጥሻለሁ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሄለን አባት ማን እንደሆነ በራስሽ ድምፅ ቀድተሽ በእጄ እንድሰጪኝ ካለበለዝያ እየፈራሽው ያለው ነገር ሁሉ ይሆናል ይሄንን ማድረግ ከቻልሽ ግን ከልጅሽ ጋር ያለው ነገር አያሳስብሽ
‹‹አሺ እግዜር ይስጥልኝ››ብላ ቅዝቅዝ እንዳለች…. በእንባ እንደታጠበች..በስጋት እንደተወጠረች….እቤቱን ለቃ ወጥታ ሄደች
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍1
#ውይ_ወንዶች አሉ ሴቶች እውነታቸውን ነው
ቀልዱ የፈረንጅ ነው ወደኛ ስናመጣው እንዲህ ይነበባል .....
ሰውየው ሚስቴ ጠፋችብኝ ብሎ ፖሊስ ጣቢያ ያመለክታል ...በቃ እንደወጣች የውሃ ሽታ ሆነች ሳምንቷ ...እና ፖሊስ ስለጠፋችው ሚስት አንዳንድ ምልክት ጠየቀ
የባለቤትህ የአይኗ ቀለም ምናይነት ነው ?
የአይኗ ቀለም ? ....እኔጃ
የፀጉሯ ቀለም .?...
እኔጃ አንዳንዴ ቀይ ትቀባዎለች አንዳንዴ ብራውን ....ጎልደን ለመጨረሻ ጊዜ ምን እንደቀባችው አላስታውስም
ቁመቷ ?
ቁመቷ ....እኔጃ ያው አልጋ ላይ እኩል ነበርን
ስሟ ...ስሟ እ ....ርብቃ !
የአባቷ ስም ?
እኔጃ !
የልደቷ ቀን ?
እኔጃ !
ለመጨረሻ ጊዜ የለበሰችው ልብስ ...
አላስታውስም ! ግን የምወዳትን መኪና ይዛ ነው የወጣችው !
እሽ የመኪናዋን ልዩ ምልክት ትነግረኝ ?
በሚገባ ! መኪናየ ቀይ የ2005 ደብል ጋቢና ሃይሉክስ ነች በቀኝ በኩል ባለፈው ፒያሳ አንዱ ሚኒባስ ነካ አድርጓት ጭረት አላት ..ሁለት ጎማ ከስድስት ወር በፊት ቀይሬላታለሁ ታርጋ ቁጥሯ 54397 ነው .....መስተዋት መወልወያው የቀኙ ተበላሽቷል ልክ ሚስቴ ይዛት የሄደች ቀን 12 ሺህ 219 .4 ኪሎ ሜትር ተነድታ ነበር ......30 ሊትር ነዳጅም ነበራት ....
ፖሊሱ የሰውየው ከሚስቱ በላይ ለመኪናው ያለው ፍቅር ገርሞት
ችግር የለም ጌታየ መኪናህን በፍጥነት አግኝተን እንመልስልሃለን
ውይ ወንዶችና መኪና ሴቶች መኪና ያለው ወንድ ሲቀርቧችሁ አደራ .....እኛ እግረኞችን ግን ውድድድ ....እየነፈሰብን ዎክ ማድረግ ይሻላል :)ምንም ቢሆን እኛ እግረኞች ከእናተ በላይ ታክሲ ወላ ባቡር አንወድ ምናባታችን አማራጭ አለን እናተው ጋር ተያይዘን እየኳተንን "ሃኒ ዋናው ፍቅር ነው " ከማለት ውጭ
🔘አሌክስ አብርሃም🔘
ቀልዱ የፈረንጅ ነው ወደኛ ስናመጣው እንዲህ ይነበባል .....
ሰውየው ሚስቴ ጠፋችብኝ ብሎ ፖሊስ ጣቢያ ያመለክታል ...በቃ እንደወጣች የውሃ ሽታ ሆነች ሳምንቷ ...እና ፖሊስ ስለጠፋችው ሚስት አንዳንድ ምልክት ጠየቀ
የባለቤትህ የአይኗ ቀለም ምናይነት ነው ?
የአይኗ ቀለም ? ....እኔጃ
የፀጉሯ ቀለም .?...
እኔጃ አንዳንዴ ቀይ ትቀባዎለች አንዳንዴ ብራውን ....ጎልደን ለመጨረሻ ጊዜ ምን እንደቀባችው አላስታውስም
ቁመቷ ?
ቁመቷ ....እኔጃ ያው አልጋ ላይ እኩል ነበርን
ስሟ ...ስሟ እ ....ርብቃ !
የአባቷ ስም ?
እኔጃ !
የልደቷ ቀን ?
እኔጃ !
ለመጨረሻ ጊዜ የለበሰችው ልብስ ...
አላስታውስም ! ግን የምወዳትን መኪና ይዛ ነው የወጣችው !
እሽ የመኪናዋን ልዩ ምልክት ትነግረኝ ?
በሚገባ ! መኪናየ ቀይ የ2005 ደብል ጋቢና ሃይሉክስ ነች በቀኝ በኩል ባለፈው ፒያሳ አንዱ ሚኒባስ ነካ አድርጓት ጭረት አላት ..ሁለት ጎማ ከስድስት ወር በፊት ቀይሬላታለሁ ታርጋ ቁጥሯ 54397 ነው .....መስተዋት መወልወያው የቀኙ ተበላሽቷል ልክ ሚስቴ ይዛት የሄደች ቀን 12 ሺህ 219 .4 ኪሎ ሜትር ተነድታ ነበር ......30 ሊትር ነዳጅም ነበራት ....
ፖሊሱ የሰውየው ከሚስቱ በላይ ለመኪናው ያለው ፍቅር ገርሞት
ችግር የለም ጌታየ መኪናህን በፍጥነት አግኝተን እንመልስልሃለን
ውይ ወንዶችና መኪና ሴቶች መኪና ያለው ወንድ ሲቀርቧችሁ አደራ .....እኛ እግረኞችን ግን ውድድድ ....እየነፈሰብን ዎክ ማድረግ ይሻላል :)ምንም ቢሆን እኛ እግረኞች ከእናተ በላይ ታክሲ ወላ ባቡር አንወድ ምናባታችን አማራጭ አለን እናተው ጋር ተያይዘን እየኳተንን "ሃኒ ዋናው ፍቅር ነው " ከማለት ውጭ
🔘አሌክስ አብርሃም🔘
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ሀያ_አምስት
:
✍ድርሰት፦በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
ለዘመን ለፍቼ…
ውጤት ለመጨበጥ፣ጥቂት ሲቀረኝ
ሚስጥራዊው አምላክ…..
ወደ ኃላ ስቦ፣ባዶ አስቀረኝ፡፡
እኔም መች የዋዛ፣መች ተስፋ ቆርጬ
ከአንዱ ጀመርኩኝ፣በእልክ ተመስጬ፡፡
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ለጨረቃዋ ከፊል ምግባሯን አስረክባ ፀሀዮ ወደማደሪያዋ ኮብልላለች፡፡ቀኑ ቢጨልምም ጭላሎ ሆቴል ግን በሰውሰራሽ ብርሀን ደምቋል፡፡በውስጡ ከወዲያ ወዲህ የሚተረማመሱ ኮማሪቶች ቤቱን ሞልተውታል፡፡መቀመጫዎች በሙሉ በጠጩዎች ተይዘዋል፡ዲጄው ሞቅ ያሉ ሀገርኛ ሙዚቃዎችን በተከታታይ እየለቀቀ ነው፡፡እድምተኞቹ ግን ግማሾቹ ከሙዚቃው ምት ጋር ከወዲህ ወዲያ እየተውረገረጉ ይጨፍራሉ… ገሚሱ ደግሞ በየራሳቸው ጫወታ እና ሀሳብ ተጠምደዋል፡፡
ከወደ አንድ ጥግ የተቀመጡ ሶስት ሰዎችም መጠጣቸውን እየተጐነጩ በሀሳብ ሰምጠው የተኮራረፉ ጣውንታሞች መስለዋል፡፡በተለይ ሁለቱ ፊታቸው ተጨማዶ ና ዓይኖቻቸው ፈጠው ይታያሉ…ሶስተኛው ግን ምንም አንኳን በሀሳብ ቢዋጥም ፊቱ ላይ የሚነበበው ግን የእርጋታ እና የአሸናፊነት እርካታ ነው፡፡ይህ ሰው ኩማደር መሀሪ ነው፡፡ሁለቱ ደግሞ የዛሬዋ ጐዶሎ ቀን ከእሱ እጅ ላይ የጣላቸው የከተማዋ ሞጃዎች አቶ ዳዊት ይግዛው እና ገመዳ ነገኦ ናቸው፡፡
እንግዲህ በሌሎች መሰል ጓደኞቻቸው እንዲህ አደረጋቸው ተብሎ ሲወራና ሲነገር የሰሙትን ዛሬ የእነሱ ዕጣ ሆኖ በራሳቸው ሊከሰት ነው፡፡በተለይ ገመዳ ነገኦ ይሄ ገጠመኝ የሞት ያህል ነው የሆነባቸው.. ምክንያቱም ለዚህ ውድቀታቸው የገዛ ልጃቸው ተባባሪ ሆኖ ሲያዩ…የገዛ አብራካቸው ክፋይ ለውድቀታቸው ቋምጦ ወደ መቀመቅ ሲጐትታቸው መታዘብ…የሞት ሞት ነው የሆነባቸው፡፡
እኚ ሁለት ሀብታሞች ኮንትሮባንድ ከኬንያ ጭነው በከተማው ሰንጥቀው ወደመሀል ሀገር ሊያስተላልፉ ሲሉ ነው እጅ ከፍንጅ የያዛቸው፡፡አሁን ኮንትሮባንድ የተጫነባቸው መኪኖች እዚሁ ሆቴል ግቢ ውስጥ ተገትረው በራሱ ሰዎች በኤልያስ እና በባሪያው እየተጠበቁ ነው፡፡እሱ ደግሞ እንሆ ከባለቤቶቹ ጋር በአንድ ጠረጵዛ ዙሪያ ተቀምጦ መጠጡን እየኮመኮመ ነው፡፡
‹‹ተጫወቱ እንጂ …መጀመሪያውኑም እኮ እንደእዚህ አይነት ስራ ስትሰሩ አንድ ቀን እንደዚህ አይነት ችግር ላይ እንደሚጥል መቼስ ከልምድ ታውቁታላችሁ….እንግዲህ ምን ይደረጋል፡፡ የመጣውን ችግር እንደአመጣጡ መወጣት ነው››ሲል አላገጠባቸው፡፡
ከሁለቱ ጠና ያሉት አቶ ገመዳ ነገኦ መናገር ጀመሩ ፤ ከዚህ ቅሌት እንዴትም ብለው በየትኛውም መስዋዕትነት መውጣት አለባቸው…ካለበለዚያ በተከበሩበት ሀገር መዋረዳቸው ነው…እሳቸው እኮ የእዚህች ከተማ የተከበሩ ኢንቨስተር፤መንግስት የሚኮራባቸው ልምታዊ ባለሀብት ናቸው…..ታዲያ ይሄንን በስንት ረብጣ ብር እና ጥረት የገነቡትን ክብራቸውን በአንዴ ገደል ሲገባ ምን ይባላል ?፡፡ ወዳጀቻቸው የሆኑ እና ከእሳቸው ጋ በክብር በየአደባባዩ እና በየስብሰባው የሚታዩት እነዛ የመንግስት ትላልቅ ባለስልጣኖች ምን ያህል ያፍሩባቸዋል ….?ባለስልጣኖቹ እንኳን ምን ያፍሩባቸዋል..አብዛኞቹ ያው እንደእሳቸው ማፈሪያዎች ናቸው…‹‹ይሄውልህ ልጄ መቼስ ሰው ሆኖ የማይሳሳት የለም… እኛም ተሳስተናል…››
አቋረጣቸው…‹‹በቃ ምንም አይነት ዝባዝንኪ ዲስኩር አልፈልግም፡፡አሁን ያልኮችሁ መተከዛችሁን አቁሙና ዘና ብላችሁ ጠጡ ብቻ ነው››ቆሌያቸውን ነው የገፈፈው፡፡‹‹ታዲያ ለምን እዚህ አመጣን…. ?ቀጥታ ፖሊስ ጣቢያ አይወስደንም ነበር?›› ሲሉ ሁለቱም በውስጣቸው ማብሰልሰላቸውን ቀጠሉ..
ኩማንደር ችላ ብሎቸው መጠጡን መምጠጥ ጀመረ…ሲጋራ አወጣና ለኩሶ እያጬሰ ስለእነሱ እያሰበ ዘነ ማለቱን ቀጠለ‹‹አዎ የስንቱን ልብ እንዳቃጠላችሁ አሁን በተራችሁ ልባችሁን እንደ እዚህ ሲጋራ አቃጥለዋለው›.›ሲል በውስጡ ዛተባቸው፡፡
ኩማደር ስለ እነዚህ ከጐኑ ስለተቀመጡት ሁለት ግለሰቦች ታሪክ በደንብ ያውቃል፡፡አዎ ሁለቱም በአባ ሽፍንፍን አማካይነት በተቋቋመው የጐዳና ተዳዳሪዎች ማቋቋሚያ ማህበር ውስጥ በህዝበ ክርስቲያኑ ተመርጠው ኮሚቴ ከሆኑ አንስቶ ይከታተላቸው ነበር፡፡ሌላው ግሞ እነሱ ላይ ትኩረት እንዲያደርግ የገፋፋው ጉዳይ አንደኛው የእሱ አጋር የሆነው የኤልያስ አባትነው፤አንደኛው የእንጀራ አባቱ የወርቅአለማው የልብ ጓደኛ በመሆኑ ነው፡፡
ኩማደር ብርጭቆ ውስጥ ያለውን የመጨረሻውን መጠጥ ጨልጦ ባዶ ካደረገ ቡኃላ አስተናጋጇን ቢል እንድታመጣ አዘዛት..ብዙም አላስጠበቀቻቸው፡፡ እየተውረገረገች ቢሉን ይዛ መጥታ አቀበለችው…ሁለቱም ሂሳቡን ሊከፍሉ እጃቸውን ኪሳቸው ውስጥ በመክተት እኔ ልክፈል እኔ በማለት እርስ በራሳቸው ሲከራከሩ ‹‹ጉቦ መሆኑ ነው?››ሲል አሸማቀቃቸው እና እራሱ ከፍሎ ቀድሞቸው ወጣ ፡፡እየተሸቆጠቆጡ ተከተሉት፡፡ወደ መኖሪያ ቤቱ ነው ይዞቸው የሄደው፡፡እንደደረሰ የወንደላጤ ቤቱን ከፍቶ ገባ ..ተከትለውት ገቡ፡፡ የውስኪ ጠርሙስን ከባታው አነሳ እና ለሁለቱም ቀድቶላቸው ለራሱም ከያዘ ቡኃላ ከፊት ለፊታቸው ተቀመጠ፡፡ በማስተዋል ሲመለከታቸው በጣም እንደተረበሹ እና ግራ እንደተጋቡ ነው ተረዳ ..ይህም በመሆኑ ተደሰተ ፡፡
‹‹በነገራችን ላይ ጉዳያችሁ በህግ ይለቅላችሁ ወይስ እዚሁ እንደራደር?››ሲል አስደንጋጭ ግን በልባቸው ሲመኙት የቆዩትን ጉዳይ በጥያቄ መልክ አቀረበላቸው፡፡
‹‹እንዴት ግልፅ አልሆነልንም?››ጠየቁት አቶ ዳዊት
‹‹ንግግሬ አጭር እና ግልጽ ነው ..እኔ በምለው ተስማምታችሁ ..የማዛችሁን አድርጋችሁ ነጻ መውጣት ትፈልጋላችሁ ወይንስ በትክክለኛው መንገድ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሄዳችሁ በሀገሪቷ ህግ መደኘት ነው የምትፈልጉት?››
‹‹አረ ቅበረን..አንተው እንደፈለግክ አድርገን?››ለእሱ መማረካቸውን በመሽቆጥቆጥ አበሰሩት
‹‹አንግዲያው ጥሩ እንጀምራ…››
‹‹አሺ እንዳልክ ››ተርበተበቱ
‹‹ይሄ አሁን የጫናችሁት ኮንትሮባንድ ዋናችሁ ስንት ብር ነው?››
‹‹ሁለት ሚሊዬን ብር አካባቢ ነው››መለሱለት አቶ ዳዊት
‹‹ሲሸጥስ?››
‹‹አራት ሚሊዬን አካባቢ ያወጣል››
‹‹አንድ ሚሊዬን ለእኔ ትከፍላላችሁ››
‹‹አረ እሺ..እሺ››ሁለቱም በአንድ ቃል በደስታ ተስማሙ……..
‹‹እሱ ብቻ አይደለም››በማለት ከስጋት ተንፈስ ያለውን መንፈሳቸውን መልሶ ደግሞ ምን ሊለን ይሆን በሚል ስጋት እንዲወጠሩ አደረጋቸው
‹‹እሺ ሌላ ምን እንታዘዝ?››በለዘበ ድምጽ ጠየቁት ገመዳ ነገኦ
‹‹ወርቅአለማው ጓደኛችሁ ነው አይደል?››
‹‹አዎ ከእኔ ይልቅ ግን ከእሱ ጋር ወዳጆች ናቸው››አሁንም መልሱን የሰጡት አቶ ገመዳ ናቸው፡፡
‹‹ለምጠይቃችሁ ጥያቄ እውነቱን እንድትነግሩኝ ነው ምፈልገው..እሱ ከእናንተ ጋር ይሄንን ስራ አይሰራም እንዴ?››
‹‹ይሰራ ነበር..አሁን ግን እርም ብሎ ካቆመ አንድ ወር አለፈው..ሶስታችንም አንድ ላይ ነበር ይብቃን… አምላክ የያዝነውን ያስበላን ብለን ለማቆም የተስማማነው..ብኃላ እሱ በቃሉ ሲፀና እኔ እና እሱ ግን ይሄው እግዜር ተዋረዱ ሲለን መሰለኝ ቆይ ይህቺን የመጨረሻ ስንል…ቆይ አንዴ ስንል ይሄው ለዚህ ተዳረግን››ሲሉ በፀፀት አንገታቸውን አቀርቅረው አብራተው ያስረዱት አቶ ዳዊት ናቸው ..
የነገሩት ነገር ግን ኩማንደሩን የሚያስደስተው አልነበረም…..ለሁለተኛ ጊዜ በእዚህ ቀለም ወርቅ በሚባል ሰውዬ መበለጡን ሲገነዘብ ውስጡ እርር ድብን አለ…አሁን እፊቱ ቁጭ ብለው ምህረቱን በሚማፀኑት ሰዎች ቦታ እሱን ማየት ነበር የሚፈልገው…ኮንትሮባንድ ሲያመላልስ እጅ ከፍንጅ ይዞት ባዶ ሊያስቀረው ዕቅዱ ነበር..ግን አሁን የሚሰማው ዜና ሀሳቡ እንደተኮላሸበት የሚያረጋግጥ መርዶ
:
#ክፍል_ሀያ_አምስት
:
✍ድርሰት፦በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
ለዘመን ለፍቼ…
ውጤት ለመጨበጥ፣ጥቂት ሲቀረኝ
ሚስጥራዊው አምላክ…..
ወደ ኃላ ስቦ፣ባዶ አስቀረኝ፡፡
እኔም መች የዋዛ፣መች ተስፋ ቆርጬ
ከአንዱ ጀመርኩኝ፣በእልክ ተመስጬ፡፡
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ለጨረቃዋ ከፊል ምግባሯን አስረክባ ፀሀዮ ወደማደሪያዋ ኮብልላለች፡፡ቀኑ ቢጨልምም ጭላሎ ሆቴል ግን በሰውሰራሽ ብርሀን ደምቋል፡፡በውስጡ ከወዲያ ወዲህ የሚተረማመሱ ኮማሪቶች ቤቱን ሞልተውታል፡፡መቀመጫዎች በሙሉ በጠጩዎች ተይዘዋል፡ዲጄው ሞቅ ያሉ ሀገርኛ ሙዚቃዎችን በተከታታይ እየለቀቀ ነው፡፡እድምተኞቹ ግን ግማሾቹ ከሙዚቃው ምት ጋር ከወዲህ ወዲያ እየተውረገረጉ ይጨፍራሉ… ገሚሱ ደግሞ በየራሳቸው ጫወታ እና ሀሳብ ተጠምደዋል፡፡
ከወደ አንድ ጥግ የተቀመጡ ሶስት ሰዎችም መጠጣቸውን እየተጐነጩ በሀሳብ ሰምጠው የተኮራረፉ ጣውንታሞች መስለዋል፡፡በተለይ ሁለቱ ፊታቸው ተጨማዶ ና ዓይኖቻቸው ፈጠው ይታያሉ…ሶስተኛው ግን ምንም አንኳን በሀሳብ ቢዋጥም ፊቱ ላይ የሚነበበው ግን የእርጋታ እና የአሸናፊነት እርካታ ነው፡፡ይህ ሰው ኩማደር መሀሪ ነው፡፡ሁለቱ ደግሞ የዛሬዋ ጐዶሎ ቀን ከእሱ እጅ ላይ የጣላቸው የከተማዋ ሞጃዎች አቶ ዳዊት ይግዛው እና ገመዳ ነገኦ ናቸው፡፡
እንግዲህ በሌሎች መሰል ጓደኞቻቸው እንዲህ አደረጋቸው ተብሎ ሲወራና ሲነገር የሰሙትን ዛሬ የእነሱ ዕጣ ሆኖ በራሳቸው ሊከሰት ነው፡፡በተለይ ገመዳ ነገኦ ይሄ ገጠመኝ የሞት ያህል ነው የሆነባቸው.. ምክንያቱም ለዚህ ውድቀታቸው የገዛ ልጃቸው ተባባሪ ሆኖ ሲያዩ…የገዛ አብራካቸው ክፋይ ለውድቀታቸው ቋምጦ ወደ መቀመቅ ሲጐትታቸው መታዘብ…የሞት ሞት ነው የሆነባቸው፡፡
እኚ ሁለት ሀብታሞች ኮንትሮባንድ ከኬንያ ጭነው በከተማው ሰንጥቀው ወደመሀል ሀገር ሊያስተላልፉ ሲሉ ነው እጅ ከፍንጅ የያዛቸው፡፡አሁን ኮንትሮባንድ የተጫነባቸው መኪኖች እዚሁ ሆቴል ግቢ ውስጥ ተገትረው በራሱ ሰዎች በኤልያስ እና በባሪያው እየተጠበቁ ነው፡፡እሱ ደግሞ እንሆ ከባለቤቶቹ ጋር በአንድ ጠረጵዛ ዙሪያ ተቀምጦ መጠጡን እየኮመኮመ ነው፡፡
‹‹ተጫወቱ እንጂ …መጀመሪያውኑም እኮ እንደእዚህ አይነት ስራ ስትሰሩ አንድ ቀን እንደዚህ አይነት ችግር ላይ እንደሚጥል መቼስ ከልምድ ታውቁታላችሁ….እንግዲህ ምን ይደረጋል፡፡ የመጣውን ችግር እንደአመጣጡ መወጣት ነው››ሲል አላገጠባቸው፡፡
ከሁለቱ ጠና ያሉት አቶ ገመዳ ነገኦ መናገር ጀመሩ ፤ ከዚህ ቅሌት እንዴትም ብለው በየትኛውም መስዋዕትነት መውጣት አለባቸው…ካለበለዚያ በተከበሩበት ሀገር መዋረዳቸው ነው…እሳቸው እኮ የእዚህች ከተማ የተከበሩ ኢንቨስተር፤መንግስት የሚኮራባቸው ልምታዊ ባለሀብት ናቸው…..ታዲያ ይሄንን በስንት ረብጣ ብር እና ጥረት የገነቡትን ክብራቸውን በአንዴ ገደል ሲገባ ምን ይባላል ?፡፡ ወዳጀቻቸው የሆኑ እና ከእሳቸው ጋ በክብር በየአደባባዩ እና በየስብሰባው የሚታዩት እነዛ የመንግስት ትላልቅ ባለስልጣኖች ምን ያህል ያፍሩባቸዋል ….?ባለስልጣኖቹ እንኳን ምን ያፍሩባቸዋል..አብዛኞቹ ያው እንደእሳቸው ማፈሪያዎች ናቸው…‹‹ይሄውልህ ልጄ መቼስ ሰው ሆኖ የማይሳሳት የለም… እኛም ተሳስተናል…››
አቋረጣቸው…‹‹በቃ ምንም አይነት ዝባዝንኪ ዲስኩር አልፈልግም፡፡አሁን ያልኮችሁ መተከዛችሁን አቁሙና ዘና ብላችሁ ጠጡ ብቻ ነው››ቆሌያቸውን ነው የገፈፈው፡፡‹‹ታዲያ ለምን እዚህ አመጣን…. ?ቀጥታ ፖሊስ ጣቢያ አይወስደንም ነበር?›› ሲሉ ሁለቱም በውስጣቸው ማብሰልሰላቸውን ቀጠሉ..
ኩማንደር ችላ ብሎቸው መጠጡን መምጠጥ ጀመረ…ሲጋራ አወጣና ለኩሶ እያጬሰ ስለእነሱ እያሰበ ዘነ ማለቱን ቀጠለ‹‹አዎ የስንቱን ልብ እንዳቃጠላችሁ አሁን በተራችሁ ልባችሁን እንደ እዚህ ሲጋራ አቃጥለዋለው›.›ሲል በውስጡ ዛተባቸው፡፡
ኩማደር ስለ እነዚህ ከጐኑ ስለተቀመጡት ሁለት ግለሰቦች ታሪክ በደንብ ያውቃል፡፡አዎ ሁለቱም በአባ ሽፍንፍን አማካይነት በተቋቋመው የጐዳና ተዳዳሪዎች ማቋቋሚያ ማህበር ውስጥ በህዝበ ክርስቲያኑ ተመርጠው ኮሚቴ ከሆኑ አንስቶ ይከታተላቸው ነበር፡፡ሌላው ግሞ እነሱ ላይ ትኩረት እንዲያደርግ የገፋፋው ጉዳይ አንደኛው የእሱ አጋር የሆነው የኤልያስ አባትነው፤አንደኛው የእንጀራ አባቱ የወርቅአለማው የልብ ጓደኛ በመሆኑ ነው፡፡
ኩማደር ብርጭቆ ውስጥ ያለውን የመጨረሻውን መጠጥ ጨልጦ ባዶ ካደረገ ቡኃላ አስተናጋጇን ቢል እንድታመጣ አዘዛት..ብዙም አላስጠበቀቻቸው፡፡ እየተውረገረገች ቢሉን ይዛ መጥታ አቀበለችው…ሁለቱም ሂሳቡን ሊከፍሉ እጃቸውን ኪሳቸው ውስጥ በመክተት እኔ ልክፈል እኔ በማለት እርስ በራሳቸው ሲከራከሩ ‹‹ጉቦ መሆኑ ነው?››ሲል አሸማቀቃቸው እና እራሱ ከፍሎ ቀድሞቸው ወጣ ፡፡እየተሸቆጠቆጡ ተከተሉት፡፡ወደ መኖሪያ ቤቱ ነው ይዞቸው የሄደው፡፡እንደደረሰ የወንደላጤ ቤቱን ከፍቶ ገባ ..ተከትለውት ገቡ፡፡ የውስኪ ጠርሙስን ከባታው አነሳ እና ለሁለቱም ቀድቶላቸው ለራሱም ከያዘ ቡኃላ ከፊት ለፊታቸው ተቀመጠ፡፡ በማስተዋል ሲመለከታቸው በጣም እንደተረበሹ እና ግራ እንደተጋቡ ነው ተረዳ ..ይህም በመሆኑ ተደሰተ ፡፡
‹‹በነገራችን ላይ ጉዳያችሁ በህግ ይለቅላችሁ ወይስ እዚሁ እንደራደር?››ሲል አስደንጋጭ ግን በልባቸው ሲመኙት የቆዩትን ጉዳይ በጥያቄ መልክ አቀረበላቸው፡፡
‹‹እንዴት ግልፅ አልሆነልንም?››ጠየቁት አቶ ዳዊት
‹‹ንግግሬ አጭር እና ግልጽ ነው ..እኔ በምለው ተስማምታችሁ ..የማዛችሁን አድርጋችሁ ነጻ መውጣት ትፈልጋላችሁ ወይንስ በትክክለኛው መንገድ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሄዳችሁ በሀገሪቷ ህግ መደኘት ነው የምትፈልጉት?››
‹‹አረ ቅበረን..አንተው እንደፈለግክ አድርገን?››ለእሱ መማረካቸውን በመሽቆጥቆጥ አበሰሩት
‹‹አንግዲያው ጥሩ እንጀምራ…››
‹‹አሺ እንዳልክ ››ተርበተበቱ
‹‹ይሄ አሁን የጫናችሁት ኮንትሮባንድ ዋናችሁ ስንት ብር ነው?››
‹‹ሁለት ሚሊዬን ብር አካባቢ ነው››መለሱለት አቶ ዳዊት
‹‹ሲሸጥስ?››
‹‹አራት ሚሊዬን አካባቢ ያወጣል››
‹‹አንድ ሚሊዬን ለእኔ ትከፍላላችሁ››
‹‹አረ እሺ..እሺ››ሁለቱም በአንድ ቃል በደስታ ተስማሙ……..
‹‹እሱ ብቻ አይደለም››በማለት ከስጋት ተንፈስ ያለውን መንፈሳቸውን መልሶ ደግሞ ምን ሊለን ይሆን በሚል ስጋት እንዲወጠሩ አደረጋቸው
‹‹እሺ ሌላ ምን እንታዘዝ?››በለዘበ ድምጽ ጠየቁት ገመዳ ነገኦ
‹‹ወርቅአለማው ጓደኛችሁ ነው አይደል?››
‹‹አዎ ከእኔ ይልቅ ግን ከእሱ ጋር ወዳጆች ናቸው››አሁንም መልሱን የሰጡት አቶ ገመዳ ናቸው፡፡
‹‹ለምጠይቃችሁ ጥያቄ እውነቱን እንድትነግሩኝ ነው ምፈልገው..እሱ ከእናንተ ጋር ይሄንን ስራ አይሰራም እንዴ?››
‹‹ይሰራ ነበር..አሁን ግን እርም ብሎ ካቆመ አንድ ወር አለፈው..ሶስታችንም አንድ ላይ ነበር ይብቃን… አምላክ የያዝነውን ያስበላን ብለን ለማቆም የተስማማነው..ብኃላ እሱ በቃሉ ሲፀና እኔ እና እሱ ግን ይሄው እግዜር ተዋረዱ ሲለን መሰለኝ ቆይ ይህቺን የመጨረሻ ስንል…ቆይ አንዴ ስንል ይሄው ለዚህ ተዳረግን››ሲሉ በፀፀት አንገታቸውን አቀርቅረው አብራተው ያስረዱት አቶ ዳዊት ናቸው ..
የነገሩት ነገር ግን ኩማንደሩን የሚያስደስተው አልነበረም…..ለሁለተኛ ጊዜ በእዚህ ቀለም ወርቅ በሚባል ሰውዬ መበለጡን ሲገነዘብ ውስጡ እርር ድብን አለ…አሁን እፊቱ ቁጭ ብለው ምህረቱን በሚማፀኑት ሰዎች ቦታ እሱን ማየት ነበር የሚፈልገው…ኮንትሮባንድ ሲያመላልስ እጅ ከፍንጅ ይዞት ባዶ ሊያስቀረው ዕቅዱ ነበር..ግን አሁን የሚሰማው ዜና ሀሳቡ እንደተኮላሸበት የሚያረጋግጥ መርዶ
👍1