አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
573 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
እንዳሉ አላውቅም!!!! ብቻ ማናቸውንም ማግኘት ትንሽዬ ማስታወሻዬ ላይ ስማቸውን ፅፎ እንደመያዝ ቀላል እንዳልሆነ ገብቶኛል። በየቀኑ ግን ወደቤቴ ስገባ ያቺን በመተሻሸት ብዛት ቀለሟን የቀየረች ማስታወሻ ደብተር ገልጬ በኑሮ ደፋ ቀና ጠላቶቼን እንዳልረሳ አስታውስባታለሁ። ቀኑ እንጂ የሚረዝመው እስከእድሜዬ ማለቂያ ድረስም ቢዘገይ እነርሱን ሳላገኝ እንደማልሞት ለራሴ በየቀኑ እነግረዋለሁ።

ህልሜን ለማሳካት (በቀልን ህልም ማለቴ አይግረማችሁ!! ያው ለማሳካት እስከምንም ጥግ የምትደክሙለት ዓላማ መግደልም ቢሆን ህልም አይደል?) አዲስአበባ ላይ ጎበዝ አላሚ ተኳሽ እና እንደንፋስ የፈጠንኩ ካራቲስት መሆን ብቻውን እንደማይበቃኝ አውቄያለሁ። አዲስ አበባ ላይ ከምንም ነገር በላይ እነዚህ ሶስቱ ወይም ከሶስቱ አንዱ ያለው አቅም አለው። ሀብት ፤ ስልጣን እና ዝና!! ከሶስቱ በጥቂቱም ቢሆን ተስፋ ያለኝ ሀብት የሚለው ላይ ቢሆንም እንዴት? የሚለውን ግን እስክደርስበት ድረስ እቅዱ አልነበረኝም። ምንም ዓይነት የቅብጠት ምኞት ስላልነበረኝ የማገኘውን ገንዘብ ለኪዳን ያስፈልገዋል የምለውን ነገር ከማሟላት የተረፈኝን አስቀምጣለሁ። ጎን ለጎን መኪና መንዳት መማር እና ከሰባተኛ ክፍል የተውኩት ትምህርት አማርኛ ከማንበብ እና መሰረታዊ የሂሳብ ስሌት ከመስራት የማያሻግር በመሆኑ ቢያንስ መሰረታዊ የቴክኖሎጂ ትሩፋቶችን መጠቀም የሚያስችለኝ እውቀት ለመገብየት ሰውየውን ተከትዬ ሆቴል እና ጭፈራ ቤት ደጅ በምገተርባቸው  ቀናት እየቀረሁም ቢሆን የማታ ትምህርት ቤት ገባሁ። ውሉ ሲጠፋብኝ ኪዳን እቤት እቤት ያስጠናኛል።

ለዓመት ከ6 ወር ደላላው እንዳለው ሰውየው በአጀብ ከመሄድ ልክፍቱ ውጪ ሀገር ውስጥ በነበረበት ጊዜ አንድም አይደለም ሊያጠቃው ጮክ ብሎ የተናገረው ሰው አልሰማሁም። ከዚህ በኋላ የሆነ ቀን ዱባይ ትልቅ ስብሰባ መኖሩን እና እዛ ሲሄድ ሀብትና ጉልበቱን ማሳየት ስለሚፈልግ ሁላችንንም አስከትሎ እንደሚሄድ ተነገረን። ፓስፖርት እንኳን ስላልነበረኝ በሰውየው ጉዳይ አስፈፃሚዎች በኩል ያለቀጠሮ ፓስፖርቴ አልቆ ለመጀመሪያ ጊዜ በሰውየው የግል አውሮፕላን ተሳፈርኩ። ይሄን ጊዜ የግድ ቀሚስ መልበስ እንዳለብኝ ሲነገረኝ ከሀገር የመውጣት ጉጉቱ ስለበለጠብኝ ተስማማሁ!! ለመጀመሪያ ጊዜ ለረዥም ቀናት ከኪዳን ተለይቼ የቆየሁበት ጊዜ ስለነበር ትቼው መሄዱ ሀሳቤን ለመቀየር እስኪፈታተነኝ ከብዶኝ ነበር። የሚከፈለኝ ብር ብዙ ማድረግ የሚያስችለኝ በመሆኑ ከኪዳን ጋር ተነጋግረን እቤት የምታግዘው ሰራተኛ ቀጥሬለት ሄድኩኝ። እስከዛ ሰዓት ድረስ ሰውየው ምን ይስራ፣ ምን ይኑረው፣ ለምን ኢትዮጵያ ይኖራል? የማወቅ ፍላጎት ኖሮኝም አያውቅም!! የግሉ አውሮፕላን እንዳለው ሳውቅ ግን የገቢ ምንጩን የማወቅ ፍላጎት ኖረኝ። ዱባይ ስንደርስ የአንድ ምግባቸው ዋጋ የእኔን የወር ደመወዝ የሚሆን ሆቴል ብቻውን የያዘው እስኪመስል አንድ ፍሎር ላይ ሰፈርን። አስተናጋጆቹ መሬት በግንባራቸው ሊነኩ እስኪቀራቸው ሰግደው ነው ሰላምታ የሚያቀርቡት።

ሰውየው በሀብቱ የተፈራ እና የተከበረ ልጥጥ ነው። የተለያዩ ሀገራት ላይ ለቁጥር የታከቱ ንብረቶች እና ኢንቨስትመንቶች ባለቤት ነው። በአረብ ሀገራት ውስጥ ታላቅ የተባለ የነዳጅ ካምፓኒ ውስጥ ትልቅ ስቶክ ያለው ባለስልጣኖቹ ሁሉ የሚሽቆጠቆጡለት ሰው መሆኑን ስብሰባው አዳራሽ ሲገባ አስተዋልኩ። አዲስአበባ የሚኖረው ሀገሪቷ ላይ ኢንቨስት ማድረግ ፈልጎ የኢትዮጵያ መንግስት መንገዱን ስላላቀለለለት እግረመንገዱን በሴቶቻችን እየተዝናና ነው ገባ ወጣ የሚለው።

የዛን ቀን ማታ አንደኛውን አቅም (ሀብት) መገንባት እንደምችል እርግጠኛ ሆንኩ። ስብሰባውም ላይ እኔ ከውጭ ጠባቂ ነበርኩ። የተቀመሱት ናቸው አብረውት አዳራሽ የገቡት። የዛን ቀን የሚዘገንነኝን ሴትነቴን ለማሰብ በትንሹ ገርበብ ያለ ልብ ኖረኝ። ቢሆንም ሀሳቡን ለመፈፀም እሩቅ እንደሆነ እያሰብኩ በሚቀጥለው ማታ እድል ወይ አጋጣሚ ብቻ ክስተት ሆነ። ሰውየው የሁለተኛውን ቀን ስብሰባ ጨርሶ ሆቴሉ ካረፈ በኋላ ወክ ካልወጣው ብሎ ቀበጠ። እኔን ጨምሮ ስምንት ሴት እና ሁለት ጠብደል ወንድ አስከትሎ የተቀሩት ምን እንዲጠብቁ እንደሆነ ባላውቅም ሆቴል ውስጥ ሲጠብቁ እንዲቆዩ አስደርጎ ወጣ!! ከስር ከስሩ ጡል ጡል የሚል ትዕዛዙን የሚቀበል እና የሚያቀብል አንድ ሲያዩት ግዙፍ የሚመስል ሲሽለጠለጥ ቡችላ የሚያክል ሰውዬ ከስር ከስሩ አይለየውም። ከፊት አራት ሁለት ከጎን የተቀረነው ከኋላ ሆነን ከሆቴሉ ወጥተን ትንሽ እንደሄድን (እኔ መጨረሻ ላይ ነኝ) ሰው በበዛበት ጎዳና ሚኒባስ ከሚመስል ዝግ መኪና ውስጥ አንድ እንደእርሱ የለበሰ ባለሀብት የሚመስል ጥቁር ሰውዬ የሰማይ ስባሪ በሚያካክሉ ስድስት በኋላ ላይ ናይጄሪያውያን መሆናቸውን ያወቅኳቸው ወንዶች ታጅቦ ወረደ። የኛውን ሰውዬ ያጀብነው እኔን ጨምሮ ወደሽጉጣችን እጃችንን ላክን ……. ግማሾቻችንም ሰዎቹ ላይ ደቀንን!! የኛው ሰውዬ እንድንረጋጋ ምልክት ሰጥቶን ከሰውየው ጋር በወዳጅነት ሰላም ተባብለው የሰውየውም ጠባቂዎች ከኛ ጋር ተደባልቀው ሁለቱ እያወሩ መጓዝ ያዙ።

ሁላችንም የተቀላቀሉንን እንግዶች ችላ ብለን የተቀረነውን ዙሪያ ገባችንን በንቃት እየቃኘን ትንሽ እንደሄድን ባልታሰበ ቅፅበት ፍጥንጥን ያለ ፊልም የሚመስል ክስተት ሆነ። የሰማይ ስባሪዎቹ አንደኛው የኛን ሰውዬ ሌሎቹ ሁለቱን ወንዶች ጨምሮ ምናልባት ፈጣን ናቸው ያሏቸውን ጠባቂዎች ያዙ። የሚያወሩት አረብኛ ስለሆነ ጥቁሩ ባለሀብት የሚያወራው ባይገባኝም የሆነ የፈለገውን ነገር በጣም በንቀት እያየው ለኛ ሰውዬ እያስረዳው በችኮላ እየነገረው እያለ አውርዳቸው የነበረችው መኪና ዞራ አጠገባችን መጣች እና እንዲገባ ገፈታተሩት። መሳሪያ ያልተደገነብን እና አንገታችን ያልተቆለፈብን ሁላችንምኮ ሽጉጣችንን መዘናል። ግን መተኮስ እንዳንችል አለቃችን ተይዟል። በፍጥነት ለማሰብ ሞከርኩ። ከሰውየው ሁለት እርምጃ የማይሞላ እርቀት ላይ ደርሻለሁ። ግን ከፌቴ በቁመቱ ሙሉ የሚከልለኝ ሰውዬ የፊት ጠባቂዋን አንገት ይዞ ሽጉጡን ጭንቅላቷ ላይ ይዞታል። ምንም ያህል ብፈጥን አደጋ ያለው እርምጃ እንደምወስድ ቢገባኝም ፍርሃት አልተሰማኝም። እንቅስቃሴዬን ትኩረት የሚስብ ዓይነት ሳላደርግ ሽጉጤን የእኛን አለቃ ለያዘው ሰውዬ ግንባር አደረግኩ። ከጀርባ ከተያዘው ወንድ ጠባቂ ጋር ተያየን። እርምጃ ልወስድ እንደሆነ ገብቶታል። አባዬ ፣ አጎቴ ፣ እዚህ ስራ ልቀጠር ስል ደግሞ ቋንቋቸው ሳይገባኝ የተደናቆርኳቸው የሰውየው ሰዎች …… ያስተማሩኝን ኢላማ የምተገብርበት ሰዓት ሆነ። አልፈራሁም!! ምናልባት ብስት ሊፈጠር የሚችለውን ስለማላውቅ ወይም የመጀመሪያዬ ስለሆነ አላውቅም! ምንም ፍርሃት አልተሰማኝም። አለማወቅ አንዳንዴ ጥሩ ድፍረት ነው። ከኋላ የነበረው ልተኩስ እንደሆነ የገባው ጠባቂ ወከባ እና ሁከት ፈጥሮ ትኩረት ሲቀንስልኝ የሰውየውን ግንባር አገኘሁት እና በፍጥነት ከፊቴ የነበረው እግር ስር ዝቅ ብዬ በክንዴ ጉልበቱን ገጨሁት። ከጀርባ የነበረው የእኔን እርምጃ ተከትሎ በተፈጠረው ግርግር አለቃችንን መሬት ላይ ጥሎት እላዩ ላይ ወድቆ ከደነው። ሁለት ከኛ ወገን (እኔን ጨምሮ) ተመትቶ ቆስሎ አንድ ከእነርሱ ወገን ሞቶ ሁለት ቆስሎ አካባቢው በፖሊስ እና በህዝብ ግርግር ተዋክቦ እነሱ ሬሳቸውን ትተው በመጡበት መኪና አመለጡ። የተመታ ክንዴን ታክሜ ወደስራ ስመለስ ከዛን ቀን በኋላ የሰውየው የጎን ጠባቂ ሆንኩ!!
👍20
በሰውየው ዙሪያ ከገንዘብ ነክ ነገሮች በተጨማሪ ብዙ ብልግናዎች እንደሚከወኑ ያወቅኩትም በጎን መቆም ስጀምር ነው። አዲስአበባ ሲመጣ ሳሎኑ መጂልሱ ላይ ተቀምጦ የከተማው እምቡጥ እምቡጥ የመሳሰሉ ሴቶች እየመጡ እንደሚታረድ በግ ሽንጥና ዳሌያቸውን እያገላበጠ ፈትሾ ይመርጥ እና የወደዳትን ለራሱ የተቀሩትን እቤቱ መጥተው አብረውት ሲቅሙ እና ሲያጨሱ ለሚቆዩት እንግዶቹ ልክ <ምን ይምጣላችሁ?> ብሎ እንደሚያቀርበው ምግቡ ያቀርባቸዋል። መጀመሪያ ቀን ነውርነቱ አሳፈረኝ። የሴቶቹ ምንም የማፈር ስሜት ፊታቸው ያለመኖር እኔን መሬት ተሰንጥቃ እንድትውጠኝ እስከመመኘት አሳፈረኝ። ሲቆይ ልምድ ነው አላልኳችሁም? ለመድኩት። ሴቶቹ አንዱ ባለሃብት ላይ አይኔ እያየ ለሁለት የማይኮን ሲሆኑ አይኔን ሳላርገበግብ መቆም ለመድኩበት። ከዛ በኋላ እይዘዋለሁ ብዬ የማላስበውን ያህል ገንዘብ እየኖረኝ መጣ። ከሰውየው ጋር በየሀገሩ መዞርም ለመድኩ። በዞርንበት በተለይ እግሊዝኛ የሚነገርበት ሀገር ስሄድ ያለመማሬ የምር አስቆጨኝ እና እንግሊዝኛ ለመማር እቤቴ አስተማሪ ቀጠርኩ። ከዓመት በኋላ እየተመላለሰ ሰውየው ካስተማረኝ እንግሊዝኛ በላይ በልምድ በዙሪያዬ እነርሱ የሚያወሩት አረብኛ ይገባኝ እና መናገር መሞከር ጀመርኩ።

የጎን ክንፍ አጃቢ ከሆንኩ ከዓመት በኋላ የሰውየው የቅርብ ጠባቂዎች በሙሉ ሰልጥነውት እኔ ያልሰለጠንኩት ስልጠና መኖሩ ተነግሮኝ የመን ለስልጠና ሄድኩ። በየጊዜው ለቀናት ከኪዳን መራቁን እየተላመድነው መጥተናል። እስከአሁንም ቦታው የግለሰብ ይሁን የመንግስት በማይገባኝ ካምፕ በመሰለ ቦታ ስልጠና ለ6 ወር ወሰድኩ። አብዛኛው ስልጠና የወታደር ስልጠና ምን እንደሚመስል ባላውቅም እንደዛ ዓይነት ይመስለኛል። በየቀኑ ፈሴ ጢጥ እስኪል ከብዙ ወንዶች እና በጣት ቁጥር ከማይሞሉ ሴቶች ጋር የሚሰጡኝን የቴክኒክ እና የጉልበት ስልጠናዎች መውሰድ ነበር። አንዳንዴ ደግሞ ለስለላ የሚያሰለጭኑኝ እስኪመስለኝ በሰዓቱ በስርዓቱ የማይገቡኝን የጭንቅላት ስልጠናዎች እና ፈተናዎች ወሰድኩ።

ከስድስት ወር በኋላ ስመለስ የሰውየው ቀኝ እጅ ከመሆኔ በተጨማሪ የሚከፈለኝ ደሞዝ በህልሜ እንኳን አስቤው የማላውቀው ነበር። በዛ ላይ ጭኔን የሚያሳዩትን ብጣቂ ሚኒዎች ያለመልበስ መብት ተሰጠኝ እና በምትኩ ሙሉ ሱፍ በሱሪ መልበስ ጀመርኩ። በገንዘቤ ሳይሆን በሰውየው ገንዘብ መኪና ተገዛልኝ እና የመኪና ባለቤት ሆንኩ። አንድ ቀን እስከዛ ቀን ድረስ ሲሄድ ያልገጠመኝ ቤት አጅቤው ሄድኩ (አሁን የእኔ የሆነው የራቁት ጭፈራ ቤት) ከፊት የሚታየውን የአዘቦት ጭፈራ ቤት የሚመስል በሙዚቃ አንድ ገበያ ህዝብ የሚውረገረግበትን አዳራሽ የሚያክል ሳሎን አልፈን ወደውስጥ በሚስጥር በር ዘለቅን። ኮሪደሩ ላይ የተቀበለን አስተናጋጅ ወደተዘጋ ክፍል ወሰደን። አራት የምንሆን ሴት ጠባቂዎቹ አጅበነው ስንቆም ክፍሉ ከእርሱ ውጪ ማንም አልነበረበትም። ተራ በተራ ሴቶቹ እየገቡ የቆመው ፖል ላይ ሲጥመለመሉ ሲያስቀይር ሌላ ስትመጣ ሲያስቀይር ሌላ ስትመጣ ቆይቶ ሁለቱን መረጠ እና ፓንት ለማለት የሚያስቸግር ክር ነገር ነገራቸው ላይ ጣል አድርገው፣ የጡታቸውን ጫፍ ብቻ የሚሸፍን ጨርቅ ጩታቸው ላይ አገልድመው ይቀነጣጠሱ ገቡ። ለምጄው የለ? እየቆየ የለበሱትን እንዲያወልቁለት አዘዘ እና ረብጣ ብር አስቀመጠ። እኛን ዞር ብለው ሳያዩ እርቃናቸውን ሆኑለት። ……

ከፖላቸው ወርደው አጓጉል ቦታ እየነካኩት ሰውየው ላይ መደነስ ጀመሩ!! እኔ ብቻ ስቀር ሌሎቹን ጠባቂዎቹን እንዲወጡ አድርጎ እንኳን በእውኔ በፊልም ባየው የሚያስመልሰኝ የሚመስለኝን ብልግና ሴቶቹን አስደረጋቸው። የዛን ቀን እየወጣሁ በሴቶቹ ፍርድ አይደለም የፈረድኩባቸው <እንዴት ያለ የማይታለፍ አበሳ ቢገጥማቸው ነው እንዲህ ራሳቸውን ለማዋረድ ግድ ያልሰጣቸው?> እያልኩ አሰብኩ። የሰውየውን ምናምን ባደረጉበት አፋቸው ምግብ ይበሉበታል? እላለሁ።

እዛ ቤት መመላለስ ያዘወትር ጀመር። አንድ ቀን ታዲያ ይገጥመኛል ብዬ በምንም አጋጣሚ ያላሰብኩት ሰው ገጠመኝ። አለቃዬን አጅቤ ከክፍሉ ስወጣ ሙሉሰው በጋርድ ታጅቦ ወደሌላ ክፍል ሲገባ አየሁት። ደንዝዤ ቆምኩ። ሰውየው እንኳን እስኪያስተውለኝ ተደነባበርኩ። እሱ አላየኝም። ምናልባት ቢያየኝም አያውቀኝም። እኔ ግን ደንግጬ እግሬ ከቆመበት አልንቀሳቀስ አለኝ!!


ይቀጥላል.........



ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ

ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
👍261
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#ክፍል_አስራ_አንድ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
////

ቀኑ ጭፍግግ ያለው ነው።እቤት ተቀምጬ ከግድግዳዬ ባሻገር ካሉት ጋሽ  ሙሉአለም ጋር  የተለመደውን የአያትና የልጅ ወሬ  ማውራት በጣም ፈልጌ ነበር ...ግን   ዛሬ ዝም እንዳሉ ነው...አንዳንዴ  እንዲህ ያደርጋቸዋል፡፡

ዝምታቸው ሶስት አራት ቀን ባስ ሲልም እስከ ሳምንት ይዘልቃል።እናም በዚህ ሁለት ቀን እየሆነ ያለው እንደዛ ነው።ያ ደግሞ ለእኔ ድብርት ይለቅብኛል። እና አሁን ለዚህ ነው እቤቴን ለቅቄ የወጣሁት። የስራ ሰዓት እስኪደርስ ሁለት ትርፍ ሰዓት አለኝ፡፡
.አይገርምም በዚህ ድህነቴ ይሄ ሁሉ ትርፍ ሰዓት ..
ኑሮዬ የሚያሻሽል መአት ነገር ልሰራበት እችል ነበር...ለምሳሌ ጀብሎ ሆኜ ሲጋራና መስቲካ ባዞር የተወሰኑ ብሮች በእርግጠኝነት አገኝ ነበር....ሊስትሮም ሆኜ ጫማ ብጠርግም እንደዛው...ግን ሰነፍ ነኝ ወይም ግብዝ ነኝ ..ዲግሪ ተመርቄ እንዴት ሊስትሮ? እንዴት ጀብሎ ?ግን ባለዲግሪ ሆኜ አስተናጋጅ መሆን ከቻልኩ ጀብሎስ መሆን ምኑ ይከብዳል? ዛሬ ደገሞ ምን አይነት ሀሳቦች ናቸው በአዕምሮዬ የሚራወጡት ?
ምንአልባት እንዲህ ምነጫነጨው ልጄ ናፍቃኝ ይሆናል..ድምፆን ከሰማው ሶስት ቀን አለፈኝ..ወይ ጉድ ለአመታት ረስቼት እንዳልነበር አሁን  እንዲህ ታሪክ ይቀየር..?.በሀሳብ ስናውዝ አንድን መኪና እንዳልገጨው ስለፈራሁ ፊት ለፊቴ ካገኘሁት ካፌ ዘው ብዬ ገባሁ እና በቅርብ ያገኘውት ጠረጰዛ ላይ ወንበር ስቤ ተቀመጥኩ።

ማኪያቶ አዝዤ ለመጠጣት እያማሰልኩ ፊት ለፊቴ ያለው ቴሌቪዥን የሚያሰራጨውን ፕሮግራም  እያየሁ ነው.፡፡:ፕሮግራሙ የተደገመ ይላል፡፡ምንአልባት ከሶስት ወይም ከአራት ቀን በፊት የተከናወነ ክንውን መሰለኝ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ለመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች የማዕረግ እድገት ሰጡ .››ይላል፡ከዚህ በፊት በቴሌቭዝን የማውቃቸውም ፤በጦርነቱ ምክንያት በየፌስቡኩ ምስላቸውና የጀግንነት ስራቸው ያነበብኩላቸው ጉምቱ የሀገሪቱ የጦር ጄኔራሎች አሉበት.፡፡እኔም እንደወትሮው የቴሌቭዝን ፕሮግረሞች በተሰላቸ መንፈስ  ሳይሆን በተነቃቃ ስሜት ነበር ስከታተል የነበረው..
የማዕረግ እድገቱ ኮረኔሮችን እና ጀኔራሎችን ያከተተ ነው..የፈረጠሙና የገዘፍ የጦር ሹሞቹን ብርጋዴር ጄኔራል፤ሜጄር ጀኔራል.፤ሌፍተራን ጄኔራል እያሉ ትከሻቸወ ላይ ማዕረጉን የሚያሳይ ኮኮብ ሲያስሩላቸው ደስ ይላል፤ይነሽጣልም፡፡፡ምን አለበት እኔም ባለፈው ምልመላ ብመዘገብና ወታደር ብሆን በዚህ ህይወት ከመርመጥመጥ አይሻልም ነበር? ብዬ እራሴን ጠየቅኩ ፡፡ጥያቄዬ አግባብ ነው ወይስ አልፎ ሂያጅ ግልብ ስሜት የፈጠረው..?መልስ ከማግኘቴ በፊት በመሀከል ነጎድጎድ ተንጓጓ፤ ፍንጥቅጣቂና ዝብርቅርቅ ቀለማት በአካባቢዬ ተረጩ፤  መብረቅ  በድንገት ወደቀ…ከመቀመጫዬ ተነሳሁ ወደእስክሪኑ አፈጠጥኩ አዎ እራሷ ነች..፡፡
ኮረኔል ዜናወርቅ ይግዛው  ወደ ብርጋድር ጀኔራልነት ተሸጋግረዋል፡፡በዛ በእውቅ ቀራፂ በአመታት ጥረትና  ልፋት የተቀረፀ የሚመስለው የታነፀና የተገናባ ሰውነቷ ላይ ያንን ባለግርማ ሞገሱ የመከላከያ ልብስ ስትለብስበት ዋው…ጠቅላይ ሚስቴሩ ፊት ቆማ ቆፍጣና ወታደራዊ ሰላምታ ሰጠች…ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደጆሮዋ ጠጋ ብለው የሆነ ነገር እያንሾካሾኩላት ማዕረጉን በትከሻዋ አጠለቁላት.
እንደ አጀማማሯ ሰላምታ  ሰጥታ  ከመድረኩ ስትወርድ ጋዜጠኛ ተቀበላት፡
‹‹ብርጋዴር ጀኔራል እንኳን ደስ ያሎት››
‹‹እንኳን አብሮ ደስ ያለን?››
‹‹ሴት ሆኖ እዚህ ትልቅ ክብር ያለው ወታደራዊ ማዕረግ ላይ በመድረሶት ምን ተሰማዎት?››
‹‹ያው ይሄ ማዕረግ በደም እና በላብ ነው የሚገኘው…ደምና ላብ ደግሞ የወንድም ሆነ የሴት ጠረኑም ቀለሙም አንድ ነው…በአጠቃላይ ሴት ስለሆንኩ ሳይሆን ስለሚገባኝ ያገኘሁት ማዕረግ ስለሆነ ደስ ብሎኛል፡፡››

ጋዜጠኛው ያልጠበቀውን መልስ ማግኘቱ በሁኔታው ያስታውቃል፡፡
‹‹ምስጋና የሚያቀርብለት ሰው ወይም አካል ካለ እድሉን ልስጦት›የሚል የተለመደ የመዝጊያ ሀሳብ አቀረበ
‹‹የእውነት  ወታደር እንድሆን እና ህልሜን እንድኖር የረዳኝን ተቋሜን አመሰግናለሁ….ሀገሬንም እንደዛው…በደሜ ቁስሏን አጥባለሁ.. በአጥንቴ በጀርባዋ የተሸከመችውን ችግሯን አክላታለሁ የሚል አላማ ነበረኝ ያንንም ያደረኩ ይመስለኛል….ወደፊትም በተለየ መልኩ ተመሳሳዩን ማድረጌን ኦቀጥላለሁ…አመሰግናለሁ፡፡›› ብላ ከእስክሪኑ ወጣች…እኔም ኪሴ ገብቼ የጣጣሁበትን የማኪያቶ ሂሳብ ጠረጳዛ ላይ አስቀመጥኩና ለብቻዬን እየለፈለፍኩ ወደቤት ተመለስኩ ተንቆራጠጥኩ ..ጨጓራዬን ለበለበኝ..ምን አስዋሻት?.የጄኔራሉ ውሽማ እንደሆነች ነበር የነገረቸኝ…?ታዲያ አሁንስ ስለአለመሆኗ ምን መረጃ አለኝ ?ብዬ እራሴን ጠየቅኩ.፡፡ውሸቷን ነዋ ውሸቷን…..ቅምጡ እንደሆነች እኮ ነበር የነገረችኝ….ስራ እንደሌላትም ነግራኝ ነበር…፡፡እንደእብድ በግትልትል ሀሳቦች ሰክሬ ቀባጠርኩ፡፡

ዘንድሮ ምን ውስጥ ነው የገባሁት…?የጄኔራል ቅመጥ አፈቀርኩ ብዬ ስሰጋና ስሸማቅ ጭራሽ እራሷ ጀኔራል…ለመሆኑ ስንት አመቷ ነው…?ስትታይ እኮ ሰላሳም የሞላት አትመስልም..መቼስ በሰላሳ አመት እዚህ ደረጃ ደርሳ እኔን አታሳቅቀኝም..እኔም እኮ ሰላሳ ሊሟለኝ ሁሉት አመት ያልሞላ ጊዜ ነው የቀረኝ…ይሄው ታዲያ እኔ ያለሁበትን እና እሷ ያለችበትን እዩት..
ግን ግላዊ ህይወቷ እንዴት ነው….?ለምን እንደዛ ታደርጋለች..?እንዴት እኔን መረጠችኝ…?ንቃኝ ነው አምናኝ…?
ግን እኮ እስከዛሬ ሶስት ለሚሆኑ ቀናቶች አብረን ተጫወትን አብረን አንድ አልጋ ላይ ተኛን እንጄ ምንም በመሀላችን የተፈጠረ አካላዊ ንክኪ ሆነ ፍቅራዊ ድርድር የለም፡፡..ዝም ብዬ ነወ የምቀባጥረው...እሷ እኔን የምትፈልገኝ ለመደበሪያ ነው..ካላባት ትልቅ ሀላፊነት እና የስራ ጫና ዘና ለማለት እና የህወትን ሌለኛውን ጀርባ ለማየት ስትፈልግ ይሆናል እንደዛ የምታደርገው….ኡኡ ላብደ ነው..፡፡ልብሴን ቀየርኩና ከቤት ወጣሁ ፡፡ሰዓቱ ስለደረሰ ወደስራ ነው የገባሁት..ከአንገት በላይ የግድ ስለሆነብኝ ብቻ ስራዬን መሰራት ጀመርኩ፡፡

ማታ አራት ሰዓት አካበቢ የደንበኞችን ትዕዛዝ ለመተግበር ከአንዱ ጠረጴዛ ወደሌላው ጠረጴዛ ስመላለስ አይኔ አንድ ነገር አየ..ጄኔራሏ እንደተራ ሰው ጅንስ ሱሪ ለብሳ ኮፍያ ያለው ቢጃማ ጃኬት አድርጋ ኮፊያውን ጭነቅላቷ ላይ ደፍታ  በአይኖቿ ጥቁር መነፅሯን ሰክታ ልክ የሰፈር ማጅረት መቺ መስላ ሚሪንዳ ቶኒኳን  ትጠጣለች፡ ፡ተንደርድሬ ስሯ ደረስኩና ጠረጴዛውን ተደገፍኩ…. አይኖቾ ላይ አፈጠጥኩባት ….ተረጋግታ ቀስ ብላ መነፅሯን አወለቀችና በፈግታ አየችኝ...ምለው ነገር ስለጠፋኝ ካጎነበስኩበት ቀና አልኩና ፊቴን ዞሬ ከመቀመጫዋ ራቅኩ…ተመልሼ ወደእዛ አልሄድኩም… .በጣም ተበሳጭቼባተለሁ፡፡
እንዲያ በተወጠረ ስሜት ላይ ሆኜ ሰዓቱ እንደምንም ገፋ፡፡ ተስተናጋጆችም አንደ በአንድ እያሉ ወጥተው አለቁ… ፡፡እሷም ምን ጊዜ እንደወጣች፤ወደየት እንደወጣች  ባላያሁበት የጊዜ ቀፅበት ከእይታዬ ተሰወረች …ሂሳብ አሰረክቤና  አንገቴን አቀርቅሬ በተከፋ ስሜት ወደቤት ሄድኩ..በራፍን ከፍቼ ገባሁ፡፡

‹‹አንተ ቀልማዳ መጣህ?››አያቴ ናቸው፡፡

ውይ ተመስጌን አያቴ መናገር ጀመሩ…

‹‹አዎ አያቴ..ግን ቢያዩ ድክም ብሎኛል››መናገር በመጀመራቸው በጣም ደስ ቢለኝም እኔ ደግሞ በተቃራኒዊ በዚህ ወቅት ምንም አይነት የመናገር አፒታይት የለኝም.፡፡ጥልቅ ምስጠት ውስጥ ገብቼ በሀሳብ መንቦራጨቅ ነው ያማረኝ፡፡
👍527🔥1🥰1
‹‹እራት በልተሀል…?ካልበላህ አለ››

‹‹አይ አያቴ በልቼያለሁ ...አሁን መተኛት ብቻ ነው የምፈልገው››

‹‹እሼ ደህና እደር፡፡ ››

‹‹እሺ›› አልጋ ላይ ከመውጣቴ በፊት መብራቱን አጠፋሁት አልጋዬ ላይ ወጣሁና ብርድልብሱን ገልጬ ጥቅልል ብዬ ተኛሁ…ግን በእንቅልፍ መሸነፍ  አልጋ ላይ እንደመውደቅ ቀላል አልነበረም፡፡ተገላበጥኩ ጭንቅላቴ ወደግርጌዬ መልሼ ሞከርኩ.. አዕምሮዬን ሞልታዋለች ..ጭለማ ውስጥ ከማፍጠጥ ውጭ አይኖቼን መክደን አልቻልኩም…፡፡
‹‹መሄድ አለብኝ››
ወሰንኩ.
ቀስ ብዬ ከአልጋዬ ወረድኩ፡፡ ልክ በውድቅት ለሊት ሊዘርፍ ሰው ቤት እንደጋባ ሌባ በአውራ ጣቴ እየረገጥኩ ወደበራፉ አመረሁ፡፡በከፍተኛ ጥንቃቃ ..ድምፅ ሳላሰማ በራፉን ከፈትኩና ወጣሁ፡፡ መልሼ ዘጋሁና ግቢውን ለቅቄ ወጣሁ..፡፡ሰዓቱ ከሊቱ 7 ሰዓት አልፏል ፡፡ወደሆቴል ነው የሄድኩት ..ዘበኞቹን በስም ጠራውና አስከፈትኩ፡፡በዚህ ሰዓት ምን አጋጥሞኝ እንደተመለስኩ ቢጠይቁኝም አልመለስኩላቸውም፡፡ ዝም ብዬ ወደውስጥ ገባሁ.፡፡ሪሴፕሽን ክፍል ሄድኩና አንኳኳሁ፡፡ ተረኛዋ ውስጥ እንደምታድር አውቃለሁ…የደነገጠና ግራ የተጋባ እርብትብተት ድምጽ ከውስጥ ይሰማኛል፡፡

‹‹ማነው?››

‹‹እኔ ነኝ ደራርቱ ›

‹‹አንተ ማን ነህ››

‹‹እዬብ ነኝ..ክፈችልኝ››

‹ስሜን ስትሰማ ተንደርድራ በሩን በረገደችው...አዎ እንደምትከፍትልኝ እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ ምክንያቱም በተለየ ሁኔታ ልትቀርበኝ ሁሌ እንደጣረች ነው.፡፡እኔ ደግሞ እንዳልገባው ሰው ቀልጄና ጎነታትዬት ጥያት እሄዳለሁ፡፡

‹‹ሰላም ነህ ምን ሆነሀል?››

‹‹ምንም አልሆንኩ››

‹‹ታዲያ ወደቤትህ አልሄድክም አንዴ?››

‹‹አልሄድኩም…ምነው እረሳሽው እንዴ ና እኔ ጋር ነው የምታድረው አላልሺኝም እንዴ?››

‹‹ንግግሬ የእውነት መስሏት ደነገጠች..አፍጥጣ አየችኝ.‹‹ባክሽ ስቀልድ ነው›› ብዬ አልፌ ወደመዝገብ ሄድኩ
ወ.ሪት ዜና-ወርቅ  204 ቁጥር‹‹ቢንጎ አድራለች ማለት ነው፡፡ አዎ እዚህ ነች››

‹‹ማን?››

ጉንጯን ቆንጠጥ አደረኩና‹‹አይ ተይው በቃ ደህና እደሪልኝ››

‹‹እ ማደሩን ተውከው.››
‹‹አይ ሌላ ቀን.. እቤትሽ ይሻላል..እዚህ ጥሩ አይደለም፤አሁን በራፉን ዝጊው››አልኩና ተንደርድሬ ወደቤርጎዎቹ አመራሁ..፡፡እያለከለኩ ደረጃውን ወጣሁ፡፡ 204 ቁጥር ይታየኛል…፡፡ቀረብኩ፡፡ መብራቱ እንደበራ ነው፡፡ ከውስጥ ምንም አይነት ድምፅ አይሰማኝም..፡፡ቀስ ብዬ በራፉን ቆረቆርኩ..
ወዲያው ‹‹ማነው?›› የሚል ቆፍጣና የሴት ድምፅ ተሰ

‹‹እኔ ነኝ..እ..›

የስሜን ሙሉ ቃል ከአንደበቴ አውጥቼ ከማጠናቄ  በፊት በራፉ ተከፈተ፡፡ የለበስኩትን ጃኬት ኮሌታ በቀኝ እጇ ጨምድዳ ወደውስጥ ጎትታ አስገባችኝና በእግሯ መልሳ በራፈን በመዝጋት ከሰውነቷ አጠበቀችኝ፡፡ ግድግዳው ላይ ገፍታ ለጠፈችኝ.. ‹‹እንዴ ምን ተፈጠረ.? አላወቀችኝም እንዴ?ጠላት መስያት ይሆን እንዴ?››ግትልትል የፍራቻ ሀሳቦች በምናቤ ተራወጡ፤ እንዴ ብፈራ ይፈረድብኛል እንዴ? እኚ ሰዎች እኮ ደም ላይ የተለከፉ ሊሆን ስለሚችል ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ ቀድሞ መተንበይ አይቻልም፡፡

ይቀጥላል
👍2714👏1
#የመኖር አካፋይ የመሞት ሲሶ መንገድ መሃል.......( ክፍል ሀያ ስምንት)
(ሜሪ ፈለቀ)

«ታውቂዋለሽ እንዴ? ምነው?» ሲለኝ
<አዎ አውቀዋለሁ! በአንዲት ሰዓት ውስጥ በፍቅር እና በደስታ ከታቀፍኩበት የቤተሰቤ እቅፍ ውስጥ አስወጥቶ ህይወቴን ያመሳቀለው ሰው ነው!> ማለት ብፈልግም …. እንኳን ከዚህም ከዛም ቃርሜ እና በ6 ወር ከስልጠናው ጋር ተምሬ የምኮላተፍበት አረብኛ ቀርቶ የራሴው አማርኛ እንኳን የህመሜን ያህል ገላጭ ቃል የለውም።

«ክፉ ሰው ነው!» ብዬ ብቻ አለፍኩት። ከዛን በኋላ ግን ለሰዓታት መረጋጋት እስኪያቅተኝ ሰውነቴ ምሬት ተፋ። ፊቴ እስኪያስታውቅበት ድረስ ያለፈው ሁሉ መጠቃት፣ እልህ ፣ ቁጣ ……. እንደአዲስ በደምስሬ ከደሜ ጋር ተዘዋወረ። እቤት ደርሰን መውጫ ሰዓቴ ደርሶ ልወጣ ስል ሌሎቹን ጠባቂዎች አስወጥቶ ብቻዬን ሊያወራኝ እንደሚፈልግ ነገረኝ። ከትዕዛዝ ውጪ ምንም አይነት ነገር አውርተን ስለማናውቅ ግር እያለኝ ተቀመጥኩ።

«ምን አድርጎሽ ነው? የሞት መልዓክ ያየሽኮ ነው የመሰልሽው!» አለኝ

«በልጅነቴ ወላጆቼን ያሳጣኝ ሰው ነው!» አልኩት በደፈናው።

«ጥላቻ ከፍቅር ያይላል። በቀልም ከወሲብ እርካታ በላይ ፍሰሀን ያጎናፅፋል!» አለ ለእኔ ይሁን ለራሱ የተናገረው መለየት በሚቸግር አነጋገር። ቀጠል አድርጎ «ድፍረትሽ ያስታውቃል። ሞትን እስካለመፍራት የሚደፍረው ውስጡ የሚገፋው ጥላቻ እና ያረገዘው በቀል ያለው ሰው ነው። ፍቅር እና ተስፋ ልቡን የሞላው ሰው ፈሪ ነው። ነገን ይፈራል፣ ማጣትን ይፈራል ፣ ሞትን ይፈራል!! በልምድ ብቻ ያገኘሽው ድፍረት እንዳልሆነ ያስታውቃል።» ያለው በትክክል የገባኝ ከብዙ ጊዜ በኋላ በቀልም ጥላቻም ገፍትረው ልቆም ያላቀድኩበት ውሳኔ ላይ ሲያቆሙኝ ነው!! ይሄን አጀንዳ አንስቼ አይደለም ከሱ ጋር ከኪዳን ጋር እንኳን የምጋራው ባላመሆኑ ዝም አልኩ።

«ብዙ ሰው ባያውቅም ሰውየው የቤቱ ባለቤት ነው! ከዚህ በኋላም ተደጋጋሚ ጊዜ ልትገጣጠሚ ስለምትችዪ እንደፕሮፌሽናል ጠባቂ የግል ስሜትሽን ውጠሽ ስርዓት ባለው መልኩ ለመታየት ሞክሪ!!» አለኝ እንደትዕዛዝ ነገር! ከዛ ሁሉ ትኩረት የሰጠሁት <የቤቱ ባለቤት> የሚለውን ነው። ያውቀዋል ማለት ነው!!?? « ምን ልታደርጊው ነው የምታስቢው?» ሲለኝ ለምን ወይም እንዴት ይሄን ጥያቄ እንደጠየቀኝ አላሰብኩትም። «እገድለዋለሁ!» ያልኩት ጮክ ብዬ መሆኑን ከእርሱ እኩል ነው የሰማሁት። የሆነ የፌዝ ነገር (ቀሽም! የሚል ዓይነት ነገር) ሳቅ ብሎ

«አትቸኩዪ! በቀል የሚጣፍጠው ሰውየው ሲሰቃይ የማየት እድል ሲኖርሽ ነው!! ከገደልሽውማ ገላገልሽው! ስንት ዓመታት ተሰቃይተሻል? ስንት ዓመታት ባሰብሽው ቁጥር ህመም ተሰምቶሻል? ለዓመታት የተሰቃየሽው ስቃይ በሱ ቅፅበታዊ ሞት ይካካሳል? ይድናል? ገደልሽው! ከዛስ? እድሜ ልክሽን እስር ቤት ትማቅቂያለሽ!! በህይወት እያለም ደስታሽን ቀምቶሽ በሞቱም ደስታሽን ቀምቶሽ! ይሄ ፍትህ ነው ብለሽ ታስቢያለሽ?» ቃላቶቹን ረጋ ብሎ የሚያወራበት ለዛ ልቡ ቀዝቃዛ እና ክፉ መሆኑን ያሳብቅበታል። ያልገባኝ ለምን እኔን እንደሚያቀሳስረኝ ነው!! ሲያወራው ግን እውነትም በቀል እሱ አፍ ላይ ትጣፍጣለች። በቀልን ሳስብ የማስብ የነበረው መግደልን እንጂ በቀል እንዲህ ተሽሞንሙና እና ረቅቃ አስቤያት አላውቅም!!! ሲያዩትኮ ሰውየው ፍፁም ትሁት እና ሳቂታ፣ ካገኘው ሁሉ ጋር ጨዋታ ወዳድ ነው የሚመስለው። ከሴት ጋር ተያይዞ ካለው ስድነቱ ውጪ እቤቱ እንግዳ ጠፍቶ የማያውቅ ቸር ነው ብዬ ነበርኮ የማስበው!

«ለድፍረቴ ይቅርታ ይደረግልኝና አንተ ብትሆን ምን ታደርጋለህ? ቤተሰብህን ፣ ህይወትህን ፣ ቤትህን ፣ ልጅነትህን የቀማህን ሰው ምን ታደርገዋለህ? በድጋሚ ስለድፍረቴ ይቅርታ!»

« ድክመቱን ማግኘት ነው!! በዛ ድክመቱ ገብተሽ የሚወደውን ነገር አንድ በአንድ መንጠቅ! ልክ በቁሙ እያለ መጀመሪያ ተራ በተራ ጣቶቹን፣ ቁስሉ ደርቆ ተሻለኝ ሲል ክንዱን ፣ ቆየት ብለሽ ሙሉ እጁን ፣ ከዛ የሌላኛው እጁን ጣቶች ፣ ክንድ ፣ ሙሉ እጅ ….. እያደረግሽ አካሉን እንደመክተፍ!! ግደዪኝ ብሎ እስኪለምንሽ ወይም ራሱን ለመግደል እስኪወስን ያለውን ማሳጣት!» ሲል የተናገረውን እያንዳንዷን ድርጊት ተግብሮት እንደሚያውቅ ነው። በትክክል እንዲገባኝ የፈለገ ይመስል ወሬውን በምልክት አጅቦ ነው አስረግጦ ያስረዳኝ። አወራሩ የጭካኔ ጥግ የሆነ ወሬ እያወራ ሳይሆን የልደት ኬክ ስለመቁረስ ዓይነት ያለ ጨዋታ እንደሚያወራ ቃላቶቹን በፍቅር ነው ምላሱ ላይ የሚያሽሞነሙናቸው። ለሆነ ቅፅበት አጠገቡ መሆኔን ሁሉ ፈራሁት!!! መልሼ ፍርሃቴ ራሴኑ አሳቀኝ እንጂ! እኔ ከእርሱ በምን ተሽዬ ነው? በተናገረው ነገር ተስቤ በቀልን እሱ በገለፀው መንገድ ጭንቅላቴ ውስጥ ላጣጥመው እኮ ሞክሬያለሁ።

«እርዳታዬን ከፈለግሽ መጠየቅ ብቻ ነው የሚጠበቅብሽ!! ስለሰውዬው ማወቅ የምትፈልጊው ነገር ካለ የሀገሩ ዜጋ አለመሆኔን አትዪ ሁሉም ቦታ አይን አለኝ፣ የሚያስፈልግሽ ገንዘብ ወይም ፋሲሊቲ ምንም ቢሆን !!» አለኝ።

«እውነትህን ነው? ለምን ልትረዳኝ ፈለግክ?» ጥርጣሬም መገረምም ጨረፍ አድርጎኝ የጠየቅኩት ጥያቄ ነበር።

«ፍትህ ሲዛባ ደስ አይለኝም!! የተፃፉ ህጎች ለሁሉም ሰው እኩል ፍትህ አይሰጡም!! ጉልበተኞችን ያሾልካሉ።» ሲለኝ የከተማው ብልጣብልጥነት ብዙም ያልዘለቀው ልቤ አመነው። ወይም ድክመቴን አግኝቶብኛል። አመስግኜው ስለሰውየው ሊጠቅመኝ የሚችል መረጃ ምንም ቢሆን እርዳታውን እንደምፈልግ ነግሬው አቋራጭ መንገድ በማግኘቴ ተደስቼ ሳልጨርስ በምትኩ ከእኔ የሚፈልገው ነገር መኖሩን ነገረኝ። በጅልነቴ ብግን ያልኩት ሰውየው እውነተኛ ማነነቱን በግልፅ አሳይቶኝ እንኳን የሚቀጥለው ጥያቄ ከደግ ልብ የመነጨ እንደሚሆን መጠበቄ!!

ልክ ልከኛ ነገር ያወራ ይመስል፣ ልክ ከእዛጋ ያን ወረቀት አቀብዪኝ እንደማለት ነገር ቀለል አድርጎ …… አንድ ከየትኛው አረብ ሀገር እንደሆነ የማላውቀው አዘውትሮ እሱጋ የሚመጣ ሰውዬ ስለሚቋምጥልኝ ከእርሱ ጋር በመተኛት ውለታውን እንድከፍለው ነገረኝ። በተጨማሪ ሰውየው የምፈልገውን የሚያደርግልኝ ሀብታም መሆኑን አከለበት። ለሆነ ደቂቃ ምንም የምለው ቃል ራሱ ቸግሮኝ ዝም ብዬ እንደሆነ መዓት ሳየው ቆየሁ። ትንሽ ቆይቼ ግን ከአፌ ከወጣ በኋላ የፀፀተኝን ወሬ አወራሁ!!
👍30
«አላደርገውም!! ወንድ አልወድም ከወንድ ጋር መተኛትም አልወድም!! ሴት መሆኔን እርሳው!! ህፃን ሆኜ ነው እናቴን አይኔ ስር ሲደፍሯት ያየሁት!! እንደማንኛዋም ወጣት ሴት ያለ ስሜት አይደለም ያለኝ!! ሳስበው ራሱ ትዝ የምትለኝ እናቴ ናት!! ይዘገንነኛል። ምንም ነገር ይቀራል እንጂ አላደርገውም!!» ያልኩት እንዲያዝንልኝ ነው? ፣ እንዲረዳኝ ነው? ፣ ልዋጭ ሳይፈልግ ሙሉሰውን የማጠምድበት መላ እንዲዘይድልኝ ነው? ምን አስቤ እንደሆነ አላውቅም!! ከዚህ ሁሉ ውስጥ እሱ በድፍኑ የተሰማው ሌላ ነው።

«ጭራሽ ወንድ አላውቅም እያልሽ ነው?» ከማለቱ ዓይኖቹ ሰውነቴ ላይ በመቀላወጥ ተርመሰመሱ። በጣም እየቀፈፈኝ ተነስቼ እየቆምኩ

«አዎን ምነው?» ስለው ምንም ድንቅፍ ሳይለው ከዛኛው ሰውዬ ጋር የመተኛቱን ሀሳብ እንደቀየረ (ልክ እኔ የተስማማሁ ይመስል) እና በምትኩ ከእርሱ ጋር እንድተኛና ከፈለግኩ የሙሉሰውን ጭንቅላት ከሰውነቱ ቆርጦ እንደሚያመጣልኝ ነገረኝ። ማለት በቃ በምንም የማንግባባ የተለያየ ቋንቋ የምናወራ ሰዎች መሆናችን ሲገባኝ ተነስቼ ወደቤቴ ሄድኩ። ያወራሁትን አልሰማም?

ከዛን ቀን በኋላ በአፉ ምንም ባይናገርም አስተያየቱ ተቀየረ። ዓይኖቹን ሳይነቅል ሲያፈጥብኝ ቆዳዬን ያሳክከኛል። ተስተካክዬ መቆም ያቅተኛል። ከቀናት በኋላ ሆነ ብሎ እዛ ቤት እንድንሄድ አደረገ እና በሴቶቹ ፋንታ ሙሉሰው እንዲመጣ ጠየቀ። ሙሉሰው ከአንድ ጠባቂው ጋር መጥቶ በወዳጅ ሰላምታ ማሽቃበጥ ያበዛበት ዓይነት ሰላም ብሎት ተቀመጠ። ዘለሽ እነቂው እነቂው የሚለኝን ስሜቴን ተቆጣጥሬ ቆምኩ። ሆነ ብሎ እሱ ፈላጭ ቆራጭ መሆኑን ሊያሳያኝ ያደረገው ነገር እንደሆነ ያስታውቅበታል። ቢገጣጠም የማይቀና አማርኛ እያወራ በአይኑ እኔን ያጠናል። ሙሉሰው ወጥቶ ሲሄድ «የዚን ያህል ቀላል ነበር።» ብቻ ብሎ ዝም አለ።

ለሳምንታት በራሴ መንገድ መረጃ ላገኝ ዳከርኩ። ሌላው ቀርቶ ጭፈራ ቤቱ እንኳን ድንገት የሆነ ሰዓት ነው እንጂ የሚመጣው ማንም ሰው የሚመጣበትን ሰዓት አያውቅም። ድንገት እድለኛ ሆኜ እንኳን ባገኘው ጠባቂ አለው!! ከዛ ግን ያ ሰይጣን ሰውዬ ያቀበለኝ ሀሳብ ውስጤ ቀስ በቀስ ማደጉን ያወቅኩት። ባገኘሁት አጋጣሚ ልገድለው አለመፈለጌ ገባኝ!! ቁጭ ብዬ አስቤ አስቤ ማሰሪያዬ <ከነነፍሱ እፈልገዋለሁ! የዛን ቀን አብረውት የነበሩትን ስማቸውን የማላውቃቸውን ጨምሮ መረጃ ይሰጠኛል። እንደውም እሱ መጨረሻ ላይ ነው መሞት ያለበት!> የሚል ሆነ። ሊሆን የማይችል ቅዠት ይመስለኛል ግን ማሰብ ማቆም አቃተኝ። ግን እንዴት? አላውቅም!!!

«እሺ!» አልኩኝ ጠብ የሚል ነገር ከሌለው ብዙ ልፋት በኋላ!! «ነገር ግን በቅድሚያ የማገኘውን ነገር በዝርዝር ማወቅ እፈልጋለሁ!»

ክብሬን ሸጬ በቀል ሸመትኩበት!!! ካሰብኩት በላይ ነገሮች ቀለሉልኝና የሚያስፈልገኝ ነገር ሁሉ ኖረኝ። እኔ ግን ጎደልኩ!! ለቀናት እራሴው እሺ ብዬ ተስማምቼ የተኛሁ ሳይሆን እንደእናቴ የተደፈርኩ አይነት ስሜት ተሰማኝ። በእንባ የማላጥበው ዓይነት መቆሸሽ ሆነብኝ!! <ጥላቻ ከፍቅር ያይላል> ያለው ይሄን መሰለኝ። የገዛ ሰውነቴ የሆነ ቦታ አስቀምጬው መንቀሳቀስ ብችል አሰኘኝ። ይሄን የውስጤን ጩኸት ላለመስማት በነጋ በጠባ ሴራ መጎንጎን ሆነ ስራዬ!! ከረጠቡ አይቀር መበስበስ ነው በክፋት ተጠመቅኩ። ተንኮል አስራለሁ እፈታለሁ!! ደጋግሜ ረከስኩ!! ደጋግሜ ራሴን ረሳሁ።

ሙሉሰውን እንዲወደኝ አድርጌው አይደለም ያገባሁት!! እጁ ባይያዝበት የመጀመሪያ መግደል የሚፈልገው ሰው እኔ ነኝ!! እንዲያገባኝ አስገድጄው እንጂ!! አብዛኛው ባለስልጣን አንድ የሆነ ድክመት ወይ አንድ የሆነ ቆሻሻ ይኖረዋል። ወይ በሚስቱ ላይ ሲማግጥ ወይ በሃገር ላይ ሲማግጥ ብቻ የሆነ መረጃ ይገኝበታል። ሙሉሰው አስለፋን!! ጭራሽ ምንም ማግኘት ከበደ። በዘመድ አዝማዱ ስም ጭምር የያዛቸው ንብረቶች እና ከሀገር የዘረፋቸው ሀብቶች ማስፈራሪያ ሊሆን ቢችልም በቀላሉ በገንዘብ ሃይል መረጃዎቹን ድራሻቸውን ማስጠፋት ይችላል። የራቁት ጭፈራ ቤቱ ውስጥ በጓሮ ተሹለኩልከው የሚገቡትን ባለስልጣናት በቀላሉ በሴቶቹ ማጥመድ ይቻላል። እሱ ግን ከሴት ጋርም በፍፁም ምንም አይነት ንኪኪ የሌለው ሆኖ ተገኘ። ምናልባት ቤቱ የሱ ስለሆነ ሰራተኞቹ ባሉበት መልከስከስ ስለማይፈልግ ነው ብለን አስበን። (በሃሳቡ ተስማማሁ እንጂ ሀሳቡን የሚያመነጨው አለቃዬ ነው) እቤቱ የምትሰራዋን ሰራተኛ ያዝናት። ጭራሽ እንደውም በበጎ አድራጎት የሚታወቅ ከላዩ ላይ ዝንቡን እሽ ብል ግር ብሎ የሚወጣለት ህዝብ ያሰለፈ ሰው ነው። እጅ ወደመስጠቱ ስንቃረብ ከስንት መላምትና ልፋት በኋላ ማንም ሰውጋ የማይሰማ ማንም ሰው የማይገምተው ብልግና እቤቱ ሸሽጎ እንደሚኖር ደረስንበት። ሊያሳድገው ከገጠር ያመጣው እቤት አብሮት የሚኖር ዘመድ አለው። ደፍሮት አሁንም እያስገደደው ያባልገዋል። ከዚህ ሰውዬጋ መዋል ከጀመርኩ በኋላ ብዙ ለጆሮ የሚሰቀጥጡ ብልግናዎች ሰምቻለሁኮ ይሄ ግን ወደር የማይገኝለት ነበር። ከብዙ ሙከራ በኋላ ብልግናውን ቀረፅነው!! ይሄ ነው እጄ ላይ የጣለው!!

ለዘመናት የናፈቅኩት ቀን ተከሰተ እና ፊት ለፊት ተገናኘን። ውርደቱ እጄ ላይ እንዳለ ስነግረው ፊቱን ማየት ለቀናት ሲያቅበጠብጠኝ ነበር። እዛው የራቁት ጭፈራ ቤቱ ከአለቃዬ ጋር ሄደን እሱ ሲመጣ እንዲጎበኘው መልዕክት አስቀመጠ። እዚህ ጋር የማይገባኝ አለቃዬ በእኔ በቀል የሚሰክረው ጉዱ ነበር። ልክ መጥቶ እንደተቀመጠ።

«ሜላት እባላለሁ! ወይም ደግሞ አባቴ ባወጣልኝ ስም አምሳል!» አልኩት እና የአባቴን ማንነት ቀዬዬን እና የዛን ቀን ተፈጥሮ የነበረውን ሳላዛንፍ ነገርኩት። ምንም ታክል የፀፀት ስሜት ሽው ባላለው አነጋገር

«ጦርነት ነው የገጠምነው!! ልንስማችሁ አልነበረም የመጣነው!! እንኳን አንቺ ማን እንደሆንሽ አባትሽንም አላስታውሰውም!» ሲለኝ እሱን ለመበቀል የሄድኩት መንገድ ልክ ነው ብዬ አመንኩ። ቪዲዮውን ላኩለት እና ምንም ከማሰቡ በፊት አንድ ቅጂ አለቃዬ ጋር ፣ ሌላ ቅጂ ተቀባብሎ ሌላ ሰው ጋር መኖሩን ነገርኩት!! አንድ ነገር ሊያደርገኝ ቢያስብ መረጃውን ከመውጣት እንደማያግደው ሲያውቅ ተሰበሰበ።

«እሺ ምንድነው የምትፈልጊው? ምን ያህል?» ብሎ ራሴን የሸጥኩበትን በቀሌን በገንዘብ ተመነብኝ

«ገንዘብ አይደለም የምፈልገው!! እንድታገባኝ ነው የምፈልገው!!» ስለው በቁሙ ቃዠ።

«ቀልድ ነው የያዝሽው? ጤነኛ ነሽ?» ሲል አለቃዬ በወልካፋ አማርኛ ቅልብ አድርጎ
«ውነቷን ነው! ቀልድ የለም!» አለው።
«ምን አስበሽ ነው?»

«አታስብ ጠዋት ከእንቅልፋችን አንድ ላይ ተነስተን ፣ ደህና አደርሽ ፣ ደህና አደርክ የምንባባል፣ ቁርስ አንድ ላይ የምንበላ ሰዎች አንሆንም!! አንድ ቤትም አንኖርም! ሚዲያዎች የሚዘግቡት ሰርግ ደግሰህ እንጋባለን!! አብረን አንኖርም እንጂ የትም ቦታ ስትሄድ እጄን እጅህ ውስጥ ሻጥ አድርገህ ትሄዳለህ!! ከዛ የቀረውን እያኖርን እንመካከራለን!! ውሳኔህን እንድታሳውኝ 2 ቀን እሰጥሃለሁ። ያው አማራጭ የምትለውን በሙሉ አይተህ እንደማያዋጣ ትደርስበታለህ!!» ተወራጭቶ ወጣ!! እንደምገምተው አማራጭ ሊሆን ይችላል ብሎ የሚያስበውን ሁሉ አስቧል። ጉዱን ለማንም እንደማያዋየው ግልፅ ነው!!

ቪዲዮው ቢወጣ በመድፈር ወንጀል ብቻ አይደለም የሚከሰሰው በፍቅር ከፍ አድርጎ የሰቀለው ራሱ ህዝብ በድንጋይ ወግሮ እንደሚገድለው ያውቃል። ሰው ገደለ፣ ሀገር ከዳ ፣ ሰረቀ …… ምንም ቢባል ኸረ ምንም ጥፋት ቢሆን ይታለፍለታል። ይሄን ግን አያልፉለትም።
👍171😁1
በሁለተኛው ቀን መስማማቱን ላከብኝ!! በአደባባይ ሀገር ጉድ ያሰኘ ሰርግ ደግሶ አገባኝ!! ኪዳን ዩንቨርስቲ ገብቶ ነበር። ማንን እንደማገባ ሲያውቅ ለብዙ ሳምንታት አኩርፎኝ ነበር።

ተጋባን እንጂ አብረን አንኖርም ነበር። በአደባባይ እሱ የሚገኝባቸው ቦታዎች ግን እገኛለሁ። በዚህ አጋጣሚ ከባለስልጣኑ ማህበረሰብ ጋር የመቀላቀል እድል ኖረኝም አይደል? ሳይወድ በግዱ እየገለፈጠ <ሚስቴን ተዋወቁልኝ> ይላል። ሰዎቹን ማጥናት ተጨማሪ ስራዬ ሆነ። የመጀመሪያ ስራዬ የነበረው ሌሎቹን የአባቴን ገዳዮች ራሱ እንዲነግረኝ ማድረግ ነው። የድሮ አብሮአደጎቹጋ ሁሉ ደውሎ የዛን ቀን አብረውት የነበሩትን አጣራ!! የምፈልገው አንድ እሱን ሁለት እናቴ ስትደፈር መሳሪያ ይዞ ቆሞ የነበረውን ሶስት የአባቴን ሬሳ ተሻግሮት ያለፈውን አራት እኔ በመልክም በስምም የማላውቀው አባቴ ላይ የተኮሰው ሰውዬ!! አባቴ ላይ የተኮሰውን ሰውዬ እራሱ ሙሉሰው እንዲገድለው አደረግኩ! ተጨማሪ ወንጀልም እንደማስረጃ ለመያዝ!! ሰውየው <ባልታወቀ ሰው ተገድለው ተገኙ> ተብሎ ተቀበረ። የአባቴን ረሳ ተሻግሮት ያለፈው ኮቴውን ብቻ የማስታውሰው ሰውዬ ከልጅነት ቀዬዬ እልፍ ብሎ ያለች ሰፋ ያለች ከተማ ውስጥ ሹም ሆኖ ነበር የሚሰራው!! እሱን ፀጥ ለማድረግ ግርግር አላስፈለገም ነበር።

እናቴ ስትደፈር መሳሪያ ይዞ ቆሞ ሲያያት የነበረውን ሰውዬ ለራሴ ቆጥቤ አስቀመጥኩት!!
እየቆየ ቀን ቀንን ሲተካ ኮሽ ባለ ቁጥር የሚደነግጥ፣ ወኔው የተሰለበ ድንዙዝ እየሆነ መጣ። ያልሞተም ህያው ያልሆነም ድንዙዝ ሆነ። ባልደረቦቹ <ደህና ነው?> ብለው እኔን ይጠይቁኛል። <ኸረ ደህና ነው!> እላለሁ!!

ከአረቡ አለቃዬጋ እዚህጋ ተፋታን!! አንዳንዴ የሆነ ነገር ስፈልግ እደውልለታለሁ። የሚፈልገው ነገር ሲኖር ይደውልልኛል። ሊያስፈልጉኝ የሚችሉ ቁልፍ ሰዎችን መቆለፊያ ተንኮል የጠቆመኝ እሱ ነው!! ወሳኝ ስልጣን ላይ ያሉትን ሰዎች ቆሻሻ መያዝ!! እዚህ ነጥብ ላይ ከእርሱ የተሻለ ለመረጃ ቅርብ የነበርኩት እኔ ነበርኩ። ምክንያቱም የከፍተኛ ባለስልጣን ሚስት ነኛ!! የታዘዘውን ያቀርባል!! የደሳለንኝ ከውጪ ሀገር ባለሃብት ጋር ተሻርኮ የወርቅ ማዕድን የተገኘበትን መሬት ለአበባ ልማት አንድ ሀገር ሄክታር የተፈራረመበትን ከሰዎቹ ጋር የነበረውን ኮንፍራንስ የሚያሳይ ቪዲዮ ጭምር ያቀበለኝ እራሱ ነው!!!

በዚህን ወቅት ነው ብዙ ክፋቶችን ፣ ብዙ ተንኮሎችን ከዛም ዛሬ መረጃ እንዲያቀብለኝ የምጠብቀውን ሰዌን ጨምሮ ብዙ ሰዎች ያወቅኩት።

******
ከጎንጥ በፊ
ት ህይወት ያልነበረኝ ይመስል የምሄድበት ወይ የምሰራው ጠፋኝ!! ቀኑ አልገፋ ብሎኝ እሙጋ ሄጄ የተፈጠረውን አንድ በአንድ ነግሪያት ራሱ ጊዜው አልሄደም። ወደከተማ ተመልሼ ደጋግሜ ብደውልለት ስልኩ አይሰራም!! እንዲህ በአንድ ቀን ሳቄንም ተስፋዬንም ይዞብኝ እብስ የሚለው ምን ቀን ነው እንዲህ ልቤን ለራሴ ሳላስቀር የሰጠሁት? ምን ቀን ላይ ዓለሜ በእርሱ ውስጥ የታጠረው? ማልቀስ አማረኝ ከዛ ደግሞ ሽንፈት መሰለኝና ዋጥኩት። ሲመሻሽ ቤተክርስቲያን ገባሁ ግን ግራ ተጋባሁ!! ለእግዚአብሄር ስለወንድ ይፀለያል? ምን አድርግልኝ ተብሎ ነው የሚፀለየው? ተውኩት!! ዝምብዬ ለረዥም ሰዓት ተቀምጬ ወጣሁ!!

ውሸቱን ነበር! ቢወደኝ ኖሮ ሁለት ቀን ሙሉ እንደምጨነቅ እያወቀ ስልኩን አጠፋፍቶ አይጠፋም!! የእኔ መጨነቅ ይቅር እሱስ አልናፍቀውም? አሁንም እየሰለለኝ ይሆን? አዳር ያልሆነ አዳር አድሬ ጠዋት መረጃውን ላከልኝ!! መጀመሪያ ያየሁት የጎንጥን ነው!! ምንም የተለየ ነገር የለውም!! ተጨማሪ መረጃ ብሎ የጨመረው እኔ የማውቀው ነው!! ስልኩን ደወልኩ

«እንዴት ምንም ተጨማሪ ማስረጃ አታገኝም!?»

«አንቺኮ የፈረንጅ ፊልም ላይ እንደምታዪው ካልሆነ የምትይው ነገር አለሽ!! ሜላት ኢትዮጵያ ውስጥ ነን መረጃዎች በሙሉ አይመዘገቡም!! ከዛ ደግሞ ሰውዪሽ ሌላ ምንም ድብቅ ነገር የሌለው ከሆነስ?»

«ይኖረዋል!! ስለማታውቀው ነው ይኖረዋል!»

«የተቀሩትን መረጃዎች ግን አይተሻቸዋል?» አለኝ አይተሻቸው ቢሆን ኖሮ ስለሰውዬሽ አትጨቃጨቂኝም ነበር በሚል ለዛ። ስልኩን ዘግቼ የተቀረውን ፎልደር ከፈትኩ!!

«ይሄ የውሻ ልጅ አውቄዋለሁ!! እገለዋለሁ!!» አልኩ ለራሴ ጮክ ብዬ!! ኮቴን እንደነገሩ ደርቤ መኪና ውስጥ ገብቼ ወደክለቡ ነዳሁት!!

ይቀጥላል.........



ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ

ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
👍293😱2
#የዘርሲዎች_ፍቅር


#በፍቅረማርቆስ_ደስታ


#ክፍል_ስምንት


ጎይቲና ካርለት እንጨታቸውን ለቃቅመው አስረው፤ ዛፍ ስር
ተቀምጠዋል ነፋሻ ነው ቀኑ ፀሐይዋን ግን ባዘቶ ዳመና እየሸፈናት ሽቅብ ወደ ቡስካ ተራራ ያቀናል" እፅዋቱ ይወዛወዛሉ ወፎች ያዜማሉ ጎይቲም ታዜማለች ... ካርለት ደግሞ ህብረ ዝማሬውን ህሊናዋን ከፍታ ትቀዳዋለች

"ይእ ዛሬ ማታ ትልቅ ፌስታ እኮ ነው"

"ለምን?"

"አያ ደልቲ ከብት ይወጋላ! ከዚያ እየተበላ: ሸፈሮ ቡና
እየተጠጣ ይቆይና ማታ ሰማዩ ላይ በምትዋኘው ጨረቃ ልብሽ ስውር
ብሎ ጫካ እስኪገባ መጫወት ነው! ብላ ጎይቲ ከተቀመጠችበት ተነስታ እያቀነቀነች ዳሌዋን በማዞር መደነስ ጀመረች ጎይቲ ልቧ በሃዘን የተሰበረ ቢሆንም እራሷን ለማስደሰት
የምታደርገውን ጥረት ካርለት ስታይ አይ የሰው ልጅ ለምን ይሆን
ከደስታ ጊዜ ይልቅ በመከራው ጊዜ መዝፈን የሚወድ? ብላ ስታስብ


"ይእ ቁጭ ብለሽ
ታያለሽ?" ጎይቲ ካርለትን ሳቅ ብላ "ጠየቀቻት

ካርለቴ!- ልጃገረድ
ዳንስ አይታ አስችሏት ተመልካች ትሆናለች ቢባል ማን ያምናል!"

ጎይቲ እንደ ወንዶች እየሰገረች በማቀንቀን ካርለትን እንደ ልጃገረድ ደንሽ አለቻት ተነሳች ካርለት እየተሳሳቁ እንደ ወንድና
ልጃገረድ እየሆኑ ሲደንሱ ቆዩና ሮጠው ከስኬ አሸዋ ሄዱ  እዚያም
ዘፈኑን አስነኩት ከዚያ ጭሮሽ ውሃው ጎን ጎይቲ የተፈጨውን የካሮ አፈር አውጥታ በጥብጣ ካርለትን

"ይእ! ነይ ልቀባሽ?" አለቻት

"ልቀባ ብለሽ ነው ጎይቲ?"
ታሾፊያለሽ ይሆን? ዛሬማ መቅበጥሽ የት ይቀራል!"

"ከማን ጋር  ጎይቲ?"

"ይእ ተአንበሳሽ ነዋ!"

"እሱማ ተቀይሞኝ ሄዷል ..."

"ይእ! አያ ደልቲ እንዳስቀየምሽው እንደናሱ
(የጎሳው አባል ብትሆኝ ኖሮ ይመታሽ ነበር አንች ግን ፀንጋዛ (ባዕድ) ነሽ
ከብት ዝላይ ላይ ወይም ታገባሽ በኋላ ካልሆነ ዝንብሽንም እሽ ማለት ስለማይችል ራቅ ብሎ ብስጭቱን ሊያቀዘቅዝ ነው የሄደ‥

የሐመር ወንድ ሲቀየም እንደ አንበሳ ነው ጎምለል ብሎ ጫካ ይገባል እንጂ እንደ ሴት ቃል መለዋወጥ አይወድም ወይ ይማታና
ካለበለዚያም ከአጠገብሽ ይሄድና በኋላ ሁሉንም ረስቶ ይመጣል ወንድ ቂም ሲይዝ ነውር ነው!''

"እኔና ደልቲም ዛሬውኑ እንታረቃለን በይኛ?"

ይእ! እየነገርሁሽ የሐመር ወንዶችን ባህሪ ልቅም አድርጌ ነው የማውቀው" በረቱ በከብት የሞላ የአባቱን ጠላት የገደለ
የሐመር ወንድ ልቡ እንደ ክረምት ወንዝ ሞልቶ የተንቸረፈፈ ነው አያ ደልቲ እንዲያ ስለሆነ ነው ሲንጎማለል ሲያገሳ ሲጨብጥ ልቡ እንደ አዙሪት አሽከርክሮ ሳንቃ ደረቱ ላይ የሚጥል" አለቻት

"ዛሬ እድለኛ ነኛ! ካርለት ሳቅ ብላ ጎይቲን አየቻት

"ይእ! ዛሬማ የልብሽ መቦረቂያ ቀን ናት አያ ደልቲ ያን ሁሉ ጎጆ አልፎ አንች ዘንድ ለምን መጣ?ውሃ አምጭልኝስ ብሎ
ለምን ላከሽ  ሞኝት! ተኝቶ አልሞሻል ማለት ነው ተዚያ ህልሙን ሊያይ መጣ አየሽ  ስትንቀሳቀሽ ደግሞ ዳሌሽን ማዬት ፈልጎ ውሃ አምጭልኝ ብሎ ላከሽ  ህልሙ እውን መሆኑን አረጋግጦ
በዐይኖቹ የሚያረግደውን ሰውነትሽን ጎረሰው  ያን ጉርሻውን ማታ ጫካ መካከል ወስዶሽ እስቲውጠው ሲያመነዥከው ያመሻል  ዛሬ ማታ በጨረቃ ድባብ የአያ ደልቲ የጥም መቁረጫ አንች ነሽ!" ጎይቲ
በተናገረች ቁጥር ልቧ ቅልጥ ብላ የፈሰሰች ያክል ሰውነቷ ዛለ ዐይኖችዋ ተስለመለሙ ካርለትም ጎይቲ በተናገረችው ጎመጀች  ጮማ እንደሚያኝክ ሰው አፏ ደስ በሚል ፈሳሽ ተሞላ

"ጎይቲ ዛሬ አንች ለምን ከእሱ ጋር አትቀብጭም?"

"ይእ! እንዲያ በይኝ!" ብላ ጎይቲ እያጨበጨበች ሳቀችና

  "ምነው ካርለቴ ይኸማ ነውር ነው!" ብላ ኮስተር አለች

ካርለት ኮስተር ብላ ስታያት ስሜቷ ተምታታባት ኦ!
አምላኬ አጠፋሁ ይሆን! ጎይቲ ያለችው ከሐመር ማህበራዊ ህይወት
ጫፍ ላይ ነው ካላረገዘች
ተደግፋ ወደማትነሳበት
ገደል ትወድቃለች ስለዚህ
ምን አልባት የመውለድ ችግሩ የከሎ ከሆነ ብላ አስባ

"ጎይቲ ምን ችግር አለው - እስቲ ማህፀንሽንም ፈትሽው”?"

ካርለቴ በሆነማ በማን እድሌ የአባቴ ደንብ ግን አይፈቅድም" ብላ ትክዝ አለችና" ከሎ ስንቱን  የለመድሁትን ህይወት ነስቶኛል የእኔ በደል ግን የከፋ ነው ልጅ ወልዶ እንዳይስም በልጅነቱ የተሰበረው ልቡ እንዳይጠገን አደረኩት ያ
በደሌ አንሶኝ ደሞ ከደሙ ውጭ ልክዳው! የአባቴን ደንብ ከምሽር: የእሱን እምነት ከማጣ አሁኑኑ ጦሽ ብዬ እንደ ወፍ እንቁላል ለምን አልፈርጥም አለች
ካርለት የምትናገረው  ጠፋት ጓደኛዋ: አዛኝዋ መካሪዋ ጎይቲ አንተነህ ፅልመት ሊውጣት እየገሰገሰ ገው እሷ ደግሞ
በጓደኝነቷ ወደ ብርሃኑ ስባ ልታስቀራት ትፈልጋለች ከእሷ ጉተታ ጎን ባህልና ደንብ ፅልመቱ ውስጥ ሆኖ ጠምጥሞ አስሮ ወደ እሱ
እየሳባት ነው" ጎይቲ ህይወቷ በጨለማ አይዋጥም ባለኝ አቅም
ሊጥላት ከሚስባት ጋር እሳሳባለሁ ... እያለች ካርለት ስታስብ

"ካርለቴ ዙሪ ላሸክምሽ?"  ብላ ጎይቲ እንጨቱን አሸክማት የራሷንም ተረዳድተው ተሸክማ ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉ ጎይቲ
እያንጎራጎረች እየተሳሳቁ ከኋላ በጨሌ የተሽቆጠቆጠውን የፍዬል
ቆዳቸውን እያወናወኑ የማታ ጀምበር ሳትጠልቅ ለመድረስ ወደ መንደራቸው ሄዱ።

ካርለትና ጎይቲ መንደር ደርሰው ዕረፍት ከወሰዱ በኋላ ጎይቲ ካርለትን ጉያዋ አስገብታ ፀጉሯን በካሮ አፈር እንደገና እጣንና ቅቤ
አላቁጣ ስታለሳልስላት አንድ ጊዜ የሴት ጩኸት ሰሙና ተሯሩጠው
ሄዱ ጩኸቱን ወደሰሙበት  አቅጣጫ ኮቶ ቀደም ብላ የአየችውን በምልክት እያሳየቻቸው አፏን በመተምተም ዝም በሉና ተደበቁ ብላ በጆሯቸው አንሾካሾከችላቸው"
ሸረንቤ ሚስቱን ጎንበስ አድርጎ እየገረፉት ነው ካርለት ያን ስታይ ስቅጥጥ አላት" ኮቶና ጎይቲ ግን አስቂኝ ትርኢት እንደሚያዩ
ሁሉ በሳቅ ይፍነከነካሉ

ጎይቲ ለምን ይመታታል?" ካርለት አካሏ በፍርሃት
እየተንገጫገጨ ጠየቀቻቸው"

"ይእ! ሚስቱ አይደለች,"

"ብትሆንስ? አለች ካርለት ዐይኗን በየተራ ወደሁለቱም
አቅጣጫ እያንከራተተች ኮቶና ጎይቲ በካርለት ጥያቄ ሳቁባት

ይእ! ሴት ስትገረፍ ጥሩ ነዋ!" አለች ኮቶ ፈገግ በማለት ወደ ካርለት ዞራ

"ለምን?" የካርለት የግንባር ቆዳ ተጨማደደ ፊቷ ጨው
እንደነሰነሱበት ሁሉ ነጣ

"ይእ! ደግማ አታጠፋማ  ደሞ መመታት ፍቅር ነው ሴት ልጅ ባሏ ዘንድ ስትመጣ እንደ ዱባ ድፍንፍን ብላ ነው ድቡልቡሉን የሴትን ልጅ ልብና ጭን የሚበረግደው ግርፊያ ነው" ብላ ሳቀች ኮቶ

"አሁን እናንተ ስትመቱ ደስ ይላችኋል?"

"ይእ! ግርፊያ አይነት አይነት አለው በዓይነቱ ተሆነ:
ናፍቀሽ ከጠበቅሽው ደስ ይላል ለምን ደስ አይለን" አለች ኮቶ ጎይቲ ግን ዝም አለች

"አንችስ ጎይቲ?"


"እኔማ እድሜ ለእንዳንች አይነቱ ብመኝስ የታባቴን አገኘዋለሁ  እንደምትታለብ ላም አንገቴን በዚ
ለስላሳ የህፃን እጁ ይሸኝ እንጂ  እይ ይልቅ! ተመልከቱ የሚያረጋትን ..." አለች ጎይቲ ግርፊያውን በጉጉት እያየች

ሸሮምቤ ሚስቱ የሆነ ነገር ስትቀባጥር ከቆየች
ግርፊያውን አቁሞ ቀና በይ? አላት አርጩሜውን ወርውሮ በሾርቃ ከተቀመጠው ቅቤ በቀኝ እጁ ጣት ጠንቁሎ ጀርባዋን ቀባ ቀባ አደረገላት„ ሚስቱ ግን ቆጣ ቆጣ ትላለች እንባዋን እየጠረገች።

ካርለት ለተገረፈችው ሴት አዘነችላት በመጨረሻ ግን እጅዋን ጎትቶ ወደ ጎጆው ይዟት ገባ ጎይቲና ኮቶ ተያይተው ከልባቸው
ተሳሳቁ

"ምንድነው?" ካርለት የባሰ ግራ ተጋባች

"ይእ! ቆጣ ቆጣ ስትል አላየሻትም አሁን ትንሽ ቆይተሽ ብታያት ቁጣዋ በደስታ ተተክቶ ታገኛታለሽ "
👍251🔥1
"ለምን ጎትቷት ገባ  እናንተስ ለምን ተሳሳቃችሁ?"  ስትል
ካርለት  ኮቶ እየሳቀች

"ይእ! ጎይቲ ለዚች ለጅልሽ የሚሆነውን ውሰጂና አሳያት  እኔ ልሂድ ኧረ እሳቱ ይጠፋብኛል ... ብላ ሮጠች  እየሳቀች።

ካርለት የሚፈፀመው ሁሉ የገባት መሆኗ ያስታውቃል
የሞኝ ሳቋን እነሱ ሲያቆሙ ጀመረች ወዲያው የአረጀውን ትዝታዋን

በአይነ ህሊናዋ ደቅና ዣክ የተባለው አሜሪካዊ እንደንስ ብሎ
መቀመጫዋን እየደበደበ: ዳሌዋን እያሸ መናገር አቅቷት ወደ መኝታ
ክፍሉ የወሰዳትና አስጨናቂው የአልጋ ላይ ጨዋታ ትዝ አላት
የፍቅር ስሜት እንደ ምስማር ሲደበድቡት ይሆን የሚገባው አለች
ከነበረችበት ሃሳብ ስትነቃ

"ጎይቲ መጀመሪያ ምን አጥፍታ ይሆን የመታት?"

ይእ! ገና አዲስ ሙሽራ ናት  ሶስት ወር ሙሉ አላየችውም መገናኘት ከጀመሩ ገና ሁለት ሣምንታቸው ነው ይነፋፈቃሉ ሚስት ናፍቆቷን የምትገልፀው በሆነ ባልሆነው በመበሳጨት ነው።ባል ደግሞ ፍቅሩን በግርፊያ ይገልፃል ሐመር ላይ የባልሽን መጠጫ
ሾርቃ ማፅዳት፥ ቤቱን መጥረግ: የከብቶችን እበት ማፈስ: የወተት ማለቢያውን ማጠን እንደሚገባሽ የባልሽ እናት እንደማታውቂ ሁሉ ካላስተማሮኩሽ ይሉሻል
አባቱም በምክር
ይሉሻል፣ ያወልቁታል  አንች ግን የምትፈልጊው ድሪያ: ጨዋታ ነው‥ ያን
ችላ ካልሽ ወላጆቹ እኛ አቅቶናል እኛ አቅቶናል  አንተ
ምከራት ይሉታል ባልሽን የሱ ምክር ደግሞ የምትመኝው ግርፊያ
ነው" ወንድ ልጅ የገረፈውን ያዝንለታል ያባብላል ያቅፋል

ልብሽ የት እየሄደ ነው የወላጆቼን ምክር የማትሰሚው?" እያለ ሲመታሽ አውቀሽ መልስ አትሰጭውም
.
… ልብሽ ያለው እዚህ ነው ሌላ ቦታ? ሲልሽም ዝም
ትያለሽ ዱላሽን እየጠጣሽ
"በእርግጥ ካርለቴ! ሁለታችሁም አትተዋወቁም የአንቺ ልብ የሚያውቀው ሌላ ነው ዝም ከተባልሽ ልብሽ ለአሁኑ  ባልሽ
አያስብም እየሮጠ ከለመደው ቦታ ይከንፋል ልብሽ ወደ ባልሽ እንዲመጣ ከእሱም ጋር እንድትግባቡ ግርፊያ ጥሩ ነው እንቦሳ የእናቱን ጡት ሲጠባ ላሟ እግሯን እስክታነሳ ለምን በራሱ
ይገጫታል? ወተት ብቻ ፍለጋ ይመስልሻል? ፍቅሩን ሲሰጣት ነው ላሟን በሳግ የሚያቃትታት ያ የጉያዋ ግጭት ነው

"ሴት በባሏ እናት ወደ ባሏ ቤት ስትወሰድ እንደምትመታ ታውቃለች ያላሰብሽው ሲሆን እንጂ ያሰብሽው ቢመጣ ምኑ
ያስከፋል! አንችስ ብትሆኝ ላይጠቅምሽ ነገር ልብሽና አካልሽ ቢለያይ ምኑ ይጠቅምሻል!"

ካለምክንያት ከደበደበሽ ግን አባትሽ ዘንድ ትሄጃለሽ
አባትሽ ፍየል ይሰጥሽና

ይዘሽለት ሂጂና ተኚ ከመታሽ ዝም በይ ሁለተኛም ሶስተኛም ጊዜ ሲመታሽ ዝም በይ አሁንም ደግሞ ከመታሽ ግን
ተመልሰሽ ነይ ይልሻል" ይህንም አድርገሽ ግርፊያውን ካላቆመ
ተመልሰሽ መጥተሽ ፍየሉን በቀበሮ አላስነጠኩ ከብቱን አላጠፋሁ እየወጣ እየገባ ይደበድበኛል በአባቴ ደንብ መሰረት ቻልሁት
መደብደቡን ግን አላቆመም ትያለሽ በዚህ ጊዜ ታላቅ ወንድምሽ እህቴን ሳታጠፋ እየደበደብክ አደነቆርካት: ግራ አጋባሃት ብሎ
ከባልሽ ጋር ዱላ ይገጥማል
ከዚያ ሁለተኛ መተሃት እኔ ዘንድ ብትመጣ ዳግመኛ አታገኛትም ይለዋል"
ግርፊያውን ሳያቋርጥ  ከቀጠለና አንች ተመልሰሽ አባትሽ ዘንድ ከሄድሽ ግን ጦርነት ይገጥማሉ አንችም ሌላ ባል ሳታስቢ ፈት
ሆነሽ አባትሽ ቤት እድሜልክሽን ልብሽ ላይ በሚነደው እሳት ደረቅ
የብቸኝነት ጭራሮ እየቆሰቆስሽ ስትቀጣጠይ ትኖሪያለሽ"

"ብዙ ጊዜ ግን ባልሽ የሚመታሽ ሌላ ወንድ እንዳታስቢ፥እንድትግባቡ: እንድታከብሪው እንጂ ሌላ ክፋት የለውም ስትቆዩ
ግን ግርፊያው ይቀንሳል

ቅድም የሸሮምቤ ሚስት ሲገርፉት ዝም ያለችው ጥፋቷን አውቃ ነው?" ካርለት ጎይቲ ስትናገር ጣልቃ ገብታ ጠየቀቻት"

"ይእ! እንግዲያስ ደሞ ተተመታሽ በኋላ ባልሽ የቅሉን ማር ይከፍትና አባብሎ ይዞሽ ይወድቃል "

"የት? ጎይቲ" ቁርበት ላይ" ብላ ጎይቲ የሚያማምሩ
ጥርሶችዋን እያሳየች ስትስቅ ካርለትም
እየሳቀች ፀጉሯን
እንድትሰራት ጉያዋ ገብታ ራሷን ዘምበል አደረገችላት

"ጎይቲ አንች ታዲያ መመታቱ ጥሩ ነው ባይ ነሽ?"

"ይእ!ጥሩ ነው እንጂ ካርለቴ  ባልሽ በመታሽ ቁጥር የፍቅር ጥገትሽ ይጨምራል ለባልሽ የሚያስገሳውን ፍቅር ትሰጭዋለሽ እሱም እንደ ክረምት ዝናብ በፍቅሩ ያርስሻል ያን ጊዜ ይበልጥ
ትቀራረባላችሁ

💫ይቀጥላል💫
👍24👎1👏1
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#ክፍል_አስራ_ሁለት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


‹‹እኔ እዬብ እኮ ነኝ.›› ብዬ ቃላት ከአንደበቴ ለማውጣት አፌን ስከፍት ከንፈሯ ከንፈሬን ጎረሰው…ተአምር ነው በዚህ ሀገር ስንት ሴት ጄኔራሎች አሉ…?ከእነዚህ ውስጥ ከ ጄኔራሎች ጋር ፍቅር ለመጋራት ስንት የአዳም ልጅ እድል አግኝቷል.?.ልቤ በትዕቢት ስታብጥ ታወቀኝ…፡፡እጄን በወገቧ ዙረያ ጠምጥሜ ይበልጥ ወደሰውነቴ አጣበቅኳት..ብስጭቴ ሁሉ ከጭንቅላቴ እየተነነ አየሩን ሲሞላ ታየኝ…ውስጤ ተንፈቅፍቆ መሳቅ ጀምሯል…
ከከንፈሯን አላቃ በአንድ እጇ ብቻ ወገቤን ይዛ ወደላይ አንጠለጠለችኝና አልጋው ላይ ወረወረችኝ…፡፡ወይኔ ዛሬ በቃ እስከመጨረሻው ነው…ቆይ ልብሴን ላውልቅ ብዬ ልነሳ ቀና ስል ግንባሬ ላይ ሽጉጥ ደቅናለች..መልሼ በድንጋጤ  በመደንዝ አልጋው ላይ ተዘረርኩ፡
‹‹ሽጉጥ እንኳን ሊደቀንብኝ በህይወቴ በፊት ለፊቴ አይቼው አላውቅም በፊልም እና በፎቶ ብቻ ነው የማውቀው..እና የጋለው ሰውነቴ ቀዘቀዘ…››

‹‹እንዴ ምን አጠፋሁ..?››

‹‹ሌባ ነህ..››

‹‹እኔ እዬብ እኮ
ነኝ››ለስንተኛ ጊዜ ይሆን ስሜን የነገርኳት?፡፡

‹‹አዎ ልቤንም የሰረቅከው እዬብ የተባልከው አስተናጋጅ አንተ አይደለህ?››

‹‹ይቅርታ የእኔም ልብ እኮ የለም ›አልኳት በአሳዛኝ ድምፅ ሽጉጡን ከግንባሬ አንስታ ትራሷ ስር ሸጎጠችና ከጎኔ ተኛች

‹‹በፈጣሪ ምነው ምን አድርጌሽ ነው እንዲህ ምታስደነግጪኝ.?››

‹‹ይቅርታ››

‹‹እስከአሁን እንዴት ሳትተኚ››

‹‹አየጠበቅኩህ ነበር››
‹‹እንዴት …ወደቤት ሁሉ ሄጄ ተኝቼ ነበር.

‹‹እናስ?››

.እናማ እንቅልፍ አልወስድም ሲለኝ ተመልሼ መጣዋ››

‹‹መጀመሪያ ለምን ሄድክ? አኩርፈሀኝ ነበር አይደል?››

‹‹አዎ በጣም ነበር የተበሳጨሁብሽ ..ደግሞ ዛሬ ነው ያየሁት..ወታደር መሆንሽን ብትነግሪኝ ምን አለበት ?ለዘውም ጄኔራል.››

‹‹ምን ይጠቅምሀል… እኔ ከአንተ ጋ እየተገናኘሁ ያለሁት ጄኔራል ሆኜ ሳይሆን ዜና-ወርቅን ብቻ ሆኜ ነው..››

‹‹ኸረ ተይ በናትሽ..ከቀድሞ አውቄ ቢሆን ልቤን መች እንዲህ አዝረከርካት ነበር…››

‹‹ምን  ወታደር አይመችህም እንዴ?.››

‹‹አረ እንደዛ ማለቴ
አይደለም ግን ይከብዳል…በተለይ ለአንቺ የሚከብድ ይመስለኛል..አለ አይደለ እኔ እንጃ ብቻ.››

‹‹ለማለት የፈለከው ገብቶኛል.ግን አታስብ በቅረብ ጡረታ ልወጣ ነው..››

‹ጡረታ ምነው በዚህ ዕድሜሽ.?ለዛውም የማአረግ እድገት ባገኘሽበት ማግስት ››
‹ ምክንቱን ሌላ ጊዜ እንግርሀለሁ …ግን ከአንድ ወር ባልበለጠ ጊዜ ከሰራዊቱ እሰናበትና ሌላ የሲብል ስራ ላይ የምመደብ ይመስለኛል…››

‹‹አሁን ትንሽ ቀለል አለኝ…መቼስ ጡረታ ከወጣሽ በኃላ ችላ አትይኚም አይደል?››

‹‹አይ አልልህም….ግን አንድ ልደብቅህ ማልፈልገው ነገር አለ››

ስለጄኔራሉ ፍቅረኛዋ የሆነ ነገር ልትለኝ ነው ብዬ በታፈነ ስሜት‹‹ ምን?›› ስል ጠየቅኳት

‹‹አንተን በተመለከተ በጣም የተወዛገበ ስሜት ነው የሚሰማኝ…የሆነ ድሮ የማውቀው የጠፋ ዘመዴ ወይም ወንድሜ ነው ምትመስለኝ››ብላኝ እርፍ፡፡

‹‹ባክሽ አትቀልጂ …ይሄ ደግሞ ምን ማለት ነው?፡፡››

‹‹እኔ እንጃ …ሁል ጊዜ ላገኝህና ላቅፍህ እፈልጋለው..አግኝቼ ሳቅፍህ ደግሞ ታናሽ ወንድምሽ እኮ ነው የሚል ስሜት ይተናነቀኛል፡፡››

‹‹ምነው የጠፋ ወንድም ነበረሽ እንዴ?››

‹‹ኸረ ፍፅም.. እኔ ምንም የጠፋም ያልጠፋም ወንድም ኖሮኝ አያውቅም››
ኮስተር ብዬ‹‹ተይው በቃ ይህ የእህት ነገር እጣ-
ክፍሌ  አይደለም..ለጊዜው ጓደኞች ከሆን ይበቃል›› አልኳት …ውስጤ ግን ምንም አይነት ከእሷ ጋር ጓደኛ የመሆን ጉጉት የለውም…
በተረጋጋ አንደበት‹‹እንደዛ ከሆነ  እንተኛ››አለችኝ፡፡
‹‹ደስ ይለኛል›አልኳት፡፡
እሺ ብላ አልጋው ላይ ቆመች…የለበሰችውን ቢጃማ አወላለቀችና በሰማያዊ ፓንት ቆመች.እኔ በተኛሁበት ከስር ወደላይ እያየኋት ነው..ይገርማል በቴቪ በዛ ግርማ ሞገስ ያያት ሰው አሁን እንዲህ እርቃኗን ቆማ ከነሙሉ ውበቷና ደምግባቷ  ቢያያት ደግሞ ምን ይል ይሆን?፡እኔም በተኛሁበት ልብሴን አወላልቄ ወደጠረጳዛው ወረወርኩና ከውስጥ ገባሁ ..ቀድማኝ ገብታ ነበር፡፡ መብራቱን አጠፈሁና ከሰውነቷ ተጣበቅኩ፡፡እና ከየት እየተንቀዠቀዠች እንደመጣች ሳላውቅ የተአምር እናት በምናቤ ተሰነቀረች…የሴት ልጅን ገላ ሳቅፍ እንዲህ አይነት የሚነዝርና የሚያሾር አይንት ስሜት ሚሰማኝ ከእሷ ጋር በነበርኩበት ጊዜ ብቻ ነበር፡፡ዳሩ ነገሮች ባለምኳቸው መጠን እድገት አላሳዩም.. ሊቱን በሙሉ በመተቃቀፍ ገደብ ባይኖረውም ከዛ እልፎ ወደ  ጭን መፈላለቅ ሊያድግ አልቻለም፡፡ ‹‹በፈጣሪ አሁን እኔ ምኔነው የእሷ ወንድም የሚመስለው?››ይሁን እስቲ  ….ማምሻም ዕድሜ ነው ይባል የለ፡፡

…በማግስቱ ማታ
//
ከምሽቱም አምስት ሰዓት ከስራ መልስ ነው፡፡አልጋዬ ላይ ወጥቼ  ከብርድልብሴ ስር ገብቼ ስለነበር ስልኬን ካስቀመጥኩበት አነሳሁና  ተነጠራርቼ መብራቱን አጠፋሁ፡፡ብርድልብሱን ተከናነብኩና ሞባይሌን ከፈትኩ ፡፡ቅድም ልጄ ተአምር ልካልኝ የነበረው ቴሌግራም ከፈትኩ….እናቷ  ስለእኔ የፃፈችው ቀጣይ ፀሁፍ ነው….የእሷን ፅሁፍ ማንበብ የቡና ሱስ  ነው የሆነብኝ፡፡ ተመቻችቼ ማንበብ ቀጠልኩ፡፡

ግንቦታ 16/2008 ዓ.ም

እዬቤ ከእህቶቼ በላይ ነው ማቀርበው…ከእህቶቼም በላይ ነው የምወደው..እሱ ለእኔ የሚስጥር ተጋሪዬ ነው..እሱ ለእኔ የትምህርት ቤትም ጓደኛዬ ነው።እርቃኔን እህቶቼ ፊት ስቆም ሰውነቴን ይበላኛል...እዬቤ ፊት ሲሆን ግን የራሴን ሰውነት በራሴ አይን እያየሁ ነው የሚመስለኝ።ለምን እንደዛ ሆነ ?ለእኔም ለራሴ ግራ ይገባኛል። ለምሳሌ ልብስ ለእህቶቼ ተገዝቶ ለእኔ ባይገዛ ችግር የለውም..ለእኔ ተገዝቶ ለእሱ ላይገዛ ግን አይችልም።በቃ ያንን ልብስ በምንም አይነት አለብሰውም።እሱም እንደዛው ነው።አንዳንዴ ያው የሙት ልጅ ነው በሚል ስሌትም ከቤተሠቦቹ ቤት ኪራይ የሚገኝ ገንዘብ ስላለ በሚል  ስሌትም ብቻ ምክንያን አላውቅም ለእሱ ለብቻው ልብስ ይገዛለታል..እሺ ብሎ ይቀበልና አጣጥፎ ያስቀምጣታል"ለእኔ እስኪገዛልኝ ስድስት ወርም ቢፈጅ አይለብሳትም ።ከዛ በቤተሠብ ሁሉ ተለመደና ለሁለታችንም መግዛት እስኪችሉ ነጥለው መግዛት አቆሙ..
ከእዬቤ ጋር እድሜያችንም ተቀራራቢ በመሆኑ ክፍላችንም አንድ ነው። የምንቀመጠውም አንድ መቀመጫ ላይ ነው።ያው ግን ለትምህርት የምንሰጠው ትኩረት በጣም የተለያየ ነው።እዬቤ ከአንደኛ ክፍል አንስቶ እስከመጨረሻው አንደኛ ወይም ሁለተኛ ነው የሚወጣው..ተሳስቶ እንኳን 3 ተኛ መውጣቱን አላስታውስም ።ብዙ አያጠናም ..ክፍል ውስጥ አስተማሪ የሚያስተምረውን በፅሞና ያዳምጣል..የቤት ስራ ሳይረሳ ይሰራል፤ ፈተና ሲቃረበ ያጠናል በቃ...እኔ ግን ተውኝ "አንድ ቤት እየኖራችሁ አንድ ክፍል እየተማራችሁ አንድ አስተማሪ እያስተማራችሁ ይሄ ሁሉ  ልዩነት ምንድነው?"የአባቴ የዘወትር ጥያቄ ነበር

"ቆይ አንድ ክፍል አይደል እንዴ የምትኖሩት? ለምን አብራችሁ አታጠኑም?" አባቴ ይጠይቀዋል

‹‹ጋሼ አብረን ነው የምናጠናው..ግን እሺ አትለኝም..እያጠናን ትተኛለች..ወይም ትረብሻለች"
👍60👏1🤔1
ምንም ጥፋት ባጠፋ አንገቱ ይቀነጠሳል እንጂ እኔን ለማንም አሳልፎ አይሰጠኝም..ትምህርትን በተመለከተ  ግን ለማዬም ሆነ ለአባቴ ሁሌ እንዳቃጠረብኝና እንዳስቆጣኝ ነው"...እኔ ግን ምንም መሻሻል የማሳይ ሰው አይደለሁም።ደግሞ የሚገርመው በፈተና ቀን እንደምንም ብሎ ከእኔ ርቆ ለመቀመጥ ነው ጥረቱ...እንደምንም ተጣብቄበት ከጎኑ ብቀመጥ እንኳን ለሌሎች ልጆች ሲያስኮርጅ እኔ ብረግጠው ብጎነትለው እንደው ተሳስቶ አንድ ጥያቄ አያቀምሰኝም።አንዳንድ ጊዜ የሚገርመው ከእሱ ከምኮረጅ ልጆች ለምኜ ኮርጃለው።ከዛ ስንወጣ አኮርፈዋለሁ...ሲያናግረኝ እንባዬ እርግፋ እርግፋ ይላል፡፡

"አሁን እንዲህ ተጨንቆ ከማልቀስ..በክብር እናጥና እያልኩ ስለምንሽ ብታጠኚ አይሻልም ነበር?"

"አላጠናም...እኔ እኮ ክፋትህ ነው የሚያበሳጨኝ..ከእኔ ከልክለህ ለእነሱ ማስኮረጅህ… ካንቺ እነሱ ይበልጡብኛል ማለትህ ነው..?"

እንደትልቅ ሰው ደረቱን ነፍቶ፡"አይ ለማለት የፈለኩት ከእነሱ ጋር በፍፅም አትወዳደሪም ነው..እነሱ ደነዝ ሆኑ ሌባ ከፈለጉ ማጅራት መቺ አያገባኝም..እህቴን በተመለከተ ግን ጉዳዩ ይለያል...ከአሁኑ ኩረጃ ለመድሽ ማለት ነገ ስታድጊ ሌባ..አጭበርባሪ እና ሙሰኛ የመሆን እድልሽ ከፍተኛ ነው...እንደዛ እንዲሆን ደግሞ አልፈቅድም"ይለኛል ፡፡

"ሙሰኛ ማለት ደግሞ ምን ማለት ነው?"የማላውቀውን የፓለቲከኞች ቃል ትርጉም እንዲያብራራልኝ ጠይቀዋለው።

"የተሠጠውን ኃላፊነት ተገን አድርጎ ከሀብታሙም ከደሀውም የማይገባውን ገንዘብ ወይም መማለጃ የሚቀበል ሰው ማለት ነው...ይሄንን የሚያስረዳኝ 6 ተኛ ክፍል ሆነን ነው።ከዛ በወሬው መደመም ብቻ ሳይሆን በማብራሪያውም እኮራበታለሁ፡፡ ንዴቴ ይጠፋና እስቅለታለሁ... ሁሉን እረሳለትና እላፍው እጀምራለሁ...ከዛ በማግስቱ ነይ በይ እናጥና ይለኛል፡፡ እሺ ብዬ ጎኑ እቀመጣለሁ ...ወዲያው ግን የተለመደው መሠላቸት ውስጥ እገባለሁ... ይበሳጭብኛል...በቃ መጨረሻሽ የቤት እመቤት እና ልጅ አሳዳጊ ሆኖ መቅረት ነው?ይለኛል

"የወደፊቴን የምትወስነው አንተ ማን ስለሆንክ ነው..ለሁሉም ሰው እጣ ፋንታውን የሚደለድለው እግዚያብሄር ነው"እለዋለሁ፡

"እግዚያብሄር አንዴ ፈጥሮን ምድርና በውስጧ ያሉትን ሁሉ እንድንገዛ ሰጥቶናል..ነጋችንን የምንወስነው ዛሬ በምንሰራው ስራ ነው...እጣፋንታችንን በገዛ መዳፋችን  . ነው የምንፅፈው...ዛሬ በጥረታችንና በላባችን የምንገነባው መሠረት ላይ ነው ነገ ግድግዳና ጣሪያውን የምንሰራው..አሁን የምንሰራው  መሠረት የማይረባና ጥልቀት የሌለው ከሆነ ነገ ምን አልባት እላዩ ላይ ጎጇ ቤት ብቻ ነው ልንገነባ የምንችለው...ፎቅ ካሰብን እኛንም ይዞ እስከወዲያኛው ይሰምጣል›› ንግግሩ ሁሉ የበሰለና የትልቅ ሰው ስለሆነ እፈራዋለሁ ..እና ሁል ጊዜ እንዳሰማነኝና በሀሳብ እንደተስማማው ነው..እንደዛ በመሆኑ ደግምሞ እፍረት ይሰማኛል፡፡ እንደዚህ ለምን ይሆናል? አልፎ አልፎም ቢሆን የማላሸንፈው ለምንድነው?ስለምወደው ማሸነፍ በምችልበት ቀንም ጭምር አውቄ እየተሸነፍኩለት ነው ?ወይስ ሴት ስለሆንኩ ደካማ ሆኜ ነው..እንደዛ አይነት ድምዳሜ ላይ እንዳልደርስ ደግሞ ከእሱ በብዙ አመት የሚበልጠውን አባቴን ብዙ ጊዜ ተከራክሬ አሸንፌው አቃለሁ ..ብቻ ግራ ይገባኛል።

ሌላው ትዝ የሚለኝ እስከ አምስተኛ ክፍል ድረስ ሁሌ እሁድ እሁድ ታላቅ እህታችን ሁለታችንም አንድ ላይ ሻወር ቤት አስገብታ በየተራ እያፈራረቀች ታጥበናለች። እሷን እያበሳጨንና እያስጮህናት እርስ በርስ እንጎነታተላለን ፡፡እርስበርስ ውሀ እንረጫጫለን።እህቴ አውቃም ይሁን ወይንም ከእኔ በላይ ስለምትወደው አላውቅም እኔን ለማሸት ከምታጠፋው ጊዜ በላይ እሱ ላይ የምታጠፍው ጊዜ ይበልጣል።ታጥበን ጨርሰን የለበስነውን ፓንት አውልቀን ፎጣ ከለበስን በኃላ እኔ ፓንቴን አጥቤ እዛው አስጥቼ የመውጣት ግዴታ አለብኝ እሱ ግን አውልቆ እዛው ወለል ላይ ጥሎ መውጣት ነው የሚጠበቅበት..ከዛ እህቴ በስነ-ስርአት አጥባ ታሰጣለታለች"ብዙውን ጊዜ ከንክኖኝ ለምን ?ብዬ ጠይቄ ነበር"

"ደግሞ ከእሱ ልትፎካከሪ ነው ...ሴት እኮ ነሽ ከአሁኑ እንደዚህ አይነት ስራዎችን በራስሽ መስራት መማር አለብሽ"እባላለሁ..ቅሬታዬን ለእናቴ ሳቀርብላት"የእኔ ጎረምሳ በይ ሰው እንዳይሰማሽ"ብላ ኩም ታደርገኛለች..ለእኔ ግን መልሳቸውም ድርጊታቸው መቼም ተውጦልኝ አያውቅም።ከዛ እልክ ያዘኝና ልብስ ማጠብን በፍቅር አደርገው ጀመር ።ከአምስተኛ ክፍል ጀምሮ የራሴን ልብስ ሆነ ሰውነት በራሴ   የመከወኑን ሀላፊነት ሙሉ በሙሉ ተረከብኩ ..ስድስተኛ ክፍል ስንደርስ የእዬቤንም ልብሷች እኔነኝ የማጥበው ብዬ አብዬት አስነሳሁ.. እህቶቼ እጅ ሊሠጡ አልቻሉም..ቢሆንም እየተናጠቅኩም ቢሆን የተወሰነውን ልብሷቹን ከልብሴ ጋር እየደባለቅኩ ማጠብ ጀመርኩ ፡፡እንደዛ ማድረግ በመቻሌ አቤት የተሰማኝ ኩራት ፡፡እዬቤ የወደፊቱን እንዴት እንደሚሆን አላውቅም እንጂ ዩኒሸርሲቲ እስኪገባ አንድ ቀን ካልሲና ፓንቱን እንኳን አጥቦ አያውቅም ነበር..እኔና ሁለቱ እህቶቼ እየተሻማንና እየተናጠቅን እናጥብለታለን....በዚህ ሁኔታ ጠቅመነው ይሁን ጎድተነው ወደፊት ጊዜ ነው የሚታወቀው።
//
አንብቤ ጨረስኩ..እሷ ግን በጣም ናፈቀችኝ..ህፃንና ቀጫጫ ሆና እርቃኗን ፊቴ ከወዲህ ወዲያ ስትቅበጠበጥ..አዘናግቼ ቂጦን በእጄ መዳፍ ጧ.. አድርጌ ሳስደነግጣትና ሳስለቅሳት ትዝ አለኝና ፈገግ አልኩ፡፡
እያንዳንድን ፁሁፎቾን ባነበብኩ ቁጥር አርቄ ጥልቅ ልቤ ውስጥ የሸሸኮቸውን ትዝታዎቼን ይቀሰቀሱብኝና ጥዝጣዜው በነሀሴ ወር እንደተነሳ ሀይለኛ የጥርስ በሽታ እየነዘነዘ የምገባበት ያሳጣኛል...ትዝታው ብቻ አይደለም ናፍቆቴንም ነው የሚቀሰቅስብኝ....በተለይ ‹በዚሁ ከቀጠልሽ ወደፊት የቤት እመቤትና ልጆች አሳዳጊ ሆነሽ ነው ምትቀሪው›› ብዬ የጎረርኩባትን አሁን ባለንበት ሁኔታ ስንመዝነው ማን ትክክል አንደሆነ እዩት...ህይወት በጣም ውስብስብ እና በማይተነበይ እጣ ፋንታ የሚሾር መሆኑን ከዚህ በላይ ማስረጃ የለም…ብቻ አሁን ሁሉ ነገር ነው የናፈቀኝ፡፡ እቴቴ ትናፍቀኛለች ...እህቶቼ ሁሉም ይናፍቁኛል .. የአክስቴ ባል ጋሼ ይናፍቀኛል..እቤታችን ይናፍቀኛል..ሆያ..ሆዬ አብሬ የምጨፍራቸው የሠፈሬ ልጇች ይናፍቁኛል....

ሩትን በተመለከተ ግን ከሁሉም በላይ የማደንቅላት የማስታወት ችሎታዋን ነው...ፈፅመው ወደአእምሮዬ ጎራ ብለው የማያውቁ መአት ነገሮችን ትዝ እንዲሉኝ አድርጋለች። ታሪኩን ከስር ከስር በተከወነበት ጊዜ ፅፋው ቢሆን እሺ አሁን ግን እሷም አግብታ ከወለደች እኔም የኒቨርሲቲ ከገባሁ በኃላ  በመሆኑ የሚገርም ነው።

ስልኬን አስቀመጥኩና ኩርምትምት ብዬ ተኛው….እንቅልፍ ግን በቀላሉ ሊወስደኝ አልቻለም፡፡ለአስራ ሁለት  አመት እኮ እሷን አቅፌ ነበር የተኛሁት….ዛሬ ግን ይሄው  ትራሴን አቅፌ ተኝቻለሁ፡፡

ይቀጥላል
👍785🥰3
የመኖር አካፋይ የመሞት ሲሶ መንገድ መሃል........ ክፍል ሀያ ዘጠኝ
(ሜሪ ፈለቀ)

ሰውነቴን ያጋራሁት ወንድ ሊያስገድለኝ ከመሞከሩ በላይ የተሸነፍኩለት ሰው ስልኩን ዘጋግቶ መጥፋቱ ልቤን ሊያበድነው ይገባ ነበር? ክህደት ያውም ለመግደል እስከመሞከር የደረሰ ክህደት ይበልጣል ወይስ መተው? ጭፈራ ቤቱ እስክደርስ በዳዊት ከምናደደው እኩል በጎንጥም እየተናደድኩ ነበር የምነዳው! እንደደረስኩ በሩን በረጋግጄ ስገባ ለወትሮው የሚውልበት ቢሮው ዳዊት የለም። እሱ እስኪመጣ እየጠበቅኩ ቤቱን እየተዘዋወርኩ ማየት ጀመርኩ። ገና ረፋድ ስለሆነ ከሚያፀዱት ሰዎች ውጪ ማንም የለም!! ምንድነው የማደርገው አሁን? መቼም እንደድሮው ስራ ብዬ አልቀጥልበትም! ወይም ቢያንስ የአገልግሎቱን ዝርዝር ማስተካከል ይኖርብኛል!! ከዋናው ጭፈራ ቤት ይልቅ ከሀያ እጥፍ በላይ ገቢ የሚያስገኙት ባለሀብቱ እና ባለስልጣናቱ የሚያዘወትሯቸው በድብቅ የሚከወኑት የሴቶቹ ገላ እና የሚሸጡት አደንዛዥ እፆች ናቸው!! እነዚህ አገልግሎቶች ከተቀነሱ እንደማንኛውም የከተማዋ ጭፈራ ቤቶች ሰካራም የሚራገጥበት ወለል ብቻ ነው የሚቀረው!

እዚህ ቤት ስንቷ ወጣት የሀብታም እና የባለሀብት መዝናኛ ሆናለች!! (ስንቷ ክብሯን ሸጣ ሆዷን ሞልታለች! ወይም እናቷን አሳክማለች።) እዚህ ቤት ስንቱ ወጣት የማይወጣበት ሱስ ውስጥ ተዘፍቋል! (VIP ደንበኛ የሚባሉት ኮኬይን የሚገዙት ናቸው!! ሺሻ እንዲሰራላቸው ያዛሉ ኮኬይን ተደባልቆ ያጨሱታል። ኪሳቸውም ጤናቸውም አብሮ ይጨሳል።) እዚህ ቤት ስንቱ ባለጌ በሚስቱ ላይ ማግጧል (ስንቷ ምስኪን ሚስት እቤቷ ልጆቿን አቅፋ አልቅሳለች) ፣ እዚሁ ቤት ስንቱን ብልግና ማየት ተለማምጄ እንደ ጤንነት ቆጥሬዋለሁ!

ከሙሉሰው ጋር ተጋብተን ትንሽ እንደቆየን ፣ እንግዳ ወይ ጓደኞቹ እቤቱ ሲመጡ እቤቱ ሄጄ እንደሚስት ስብር ቅንጥስ ብሉልኝ ጠጡልኝ ማለት የለመድኩ ጊዜ ፣ እኔ ጠባቂ መሆኔ ቀርቶ በጠባቂ መታጀብ የጀመርኩኝ ጊዜ (አስፈላጊ ሆኖ አልነበረም! ለምን ጠባቂ እንደሚያጅበውም አይገባኝም!! ታይታ ካልሆነ በቀር) ፣ በቴሌቭዥን እንኳን ለማየት ወራት ከምንጠብቃቸው ባለስልጣናት ጋር የተለያዩ ክስተት እና ድግሶች ላይ የባሌን እጅ ቆልፌ መታየት የለመድኩ ጊዜ ፣ አንቱ የምለው ባለስልጣን ሚስት ባሏን ስታማልኝ የለመድኩ ጊዜ ፣ ራሴን ከእነርሱ እንደአንዳቸው ስቆጥር ያልታየ ድግስ ደግሼ እቤት እንዲታደሙልኝ ማድረግ የጀመርኩ ጊዜ፣ ………. ያኔ ጭፈራ ቤቱን በእኔ ስም እንዲያዞርልኝ አስደረግኩት። (እንደ ዓረፍተነገሩ እጥረት ሂደቱ ቀላል አልነበረም!! ትልቁ የገቢ ምንጩ ነው!! ባለስልጣናቱ የሚመጡት እሱን ስለሚያምኑት ነው!! )

ሌላው ጭንቅላቱን የምዘውርበት ጉድፉ ጭፈራ ቤቱ ነው! <ሌላውን ነውርህን ተወውና በወጣት ሴቶች ገላ እንደምትነግድ ፣ እፅ እንደምትነግድ ቢያውቅ እንደቅዱስ መልዓክ የሚያይህ ህዝብ ይቅር የሚልህ ይመስልሃል? > ራስምታት የሚቀሰቅስበት ርዕስ ነው።) ስራውን ለመልመድ ትንሽ ወራት ፈጀብኝ ግን ስለምደው ከእርሱ በተሻለ ያዝኩት ምክንያቱም እኔ ሙሉ ሀይሌን ተጠቅሜ እንጂ እንደእሱ ድብብቆሽ እየተጫወትኩ እና በትርፍ ጊዜዬ አልነበረም የምሰራው። ወደአካውንቴ ከሚያስገባልኝ ጠርቀም ያለ ገንዘብ በተጨማሪ ቁጭ ብዬ ራሴን የምሰማበት ጊዜ ስለማይሰጠኝ ወደድኩት።

እቅዴ በምፈልገው መንገድ እየሄደ ያልሞላልኝ ያን እናቴ ስትሞት መሳሪያ ዘቅዝቆ ይዞባት ተራ ሲጠብቅ የነበረ ደመኛዬን መድፋት ነበር። የሚኖረው አዲስአበባ ቢሆንም እዚህ ግባ የሚባል ማዕረግም ሀብትም ያለው ሰው አልነበረም!! ከሙሉሰው ጋር ግን በየእለቱ የሚገናኙ ሰዎች ባይሆኑም ቢያንስ የአንዳቸውን ፌስቡክ ፖስት አንዳቸው ሼር የሚደራረጉ ወዳጃሞች ናቸው!! እቅዴ ግልፅ ነበር ለሁለታችንም!! አንድ ቅዳሜ <ኸረ ተጠፋፋን ለምን ምሳ አንበላም?> ብሎ ሙሉሰው እንዲቀጥረው፣ ከዛ ሲገናኙ እኔ ባለሁበት ምሳ ልንበላ! (የመጨረሻዋን ምሳ) ስንጨርስ መኪናውን እኔ ልሾፍር ፣ ከዛማ ከከተማ አርቄ ወስጃቸው ትክክለኛ ማንነቴን ነግሬው ሬሳውን ለጅብ ጥዬ መምጣት ነበር እቅዴ!! ይሄን ከ10 ጊዜ በላይ ለሙሉሰው ነግሬዋለሁ!!

የዚህን ወቅት ከእኔ የሚያመልጥበት መንገድ መሞከሩን ተስፋ አልቆረጠበትም ነበር። በእቅዱ መሰረት መጥተን ከምሳ ወጥተን ወደመኪናችን ስንሄድ ሙሉሰው ለሰውየው እኔ ያልሰማሁትን ግን ሲመስለኝ እራሱን እንዲከላከል ወይ ልገድለው እንደሆነ አልያም ማን እንደሆንኩ ብቻ አላውቅም የነገረው መልዕክት አደባባይ ላይ ሽጉጥ አስመዝዞታል!! (ሙሉሰው አስቦበት ያደረገው ነገር መሆኑ በሚያቃጥርበት መልኩ ሰውየው መሳሪያ ስላልታጠቀ የሱን ሽጉጥ መውሰድ የሚችልበት አቋቋም ላይ ኮቱን ገልጦለት ነበር የቆመው) ሀሳቡ እሱ ማድረግ ያልቻለውን ሰውየው እኔን እንዲገድልለት ነበር። ተቀደመ እና ሰውየው እዛው ሞተ። በሰውየው ሞት ከማዘን በእኔ አለመሞት ሲበሳጭ ላየው ግራ ያጋባ ነበር። አደባባይ ላይ ስለነበር የሆነው ሁሉ የሆነው ታሰርኩ!! የዚህን ጊዜ ነው እስር ቤት ከእሙጋ የተዋወቅነው። ነገር የማትፋታ ጋዜጠኛ ነበረች። ያልሆነ ነገር እያነፈነፈች አላፈናፍን ስትላቸው ነው እረፍት እንድታደርግ ያስገቧት!! እሷ እስር ቤቱን ለምዳዋለች። ሲፈቷት ደግሞ ሲያስሯት፣ ደግሞ የሆነ ነገር ትቆፍራለች ደግሞ ይከቷታል። ለመጀመሪያ ጊዜ በህይወቴ ሳይከብደኝ ያወራኋት ፣ ሳልደብቅ ያጫወትኳት ፣ ሳትፈርድብኝ የሰማችኝ ፣ ውርደት እና ክፋቴን እንኳን የተረዳችኝ የመጀመሪያ ጓደኛዬ ሆነች። ከሶስት ወር በኋላ ምርጫ ስላልነበረው ሙሉሰው በሚኬደው ሄዶ እራሱ አስፈታኝ። እሙም ከወራት በኋላ ተፈትታ ከእስር ቤት ውጪ ጓደኝነታችን ቀጥሎ ነበር።
👍251
ወጥቼ ብዙም ሳይቆይ አንድ ባንክ ውስጥ በራሱ ፣ በእህቱ ፣ በአንድ የሩቅ ዘመዱ …… ደማምሮ የያዘውን 48% አክሲዮን ተቀበልኩት። እኔም በራሴ ፣ በኪዳን እና በእሙ ስም አደረግኩት!! የዚህን ጊዜ <እንደውም መልቀቂያ አስገብቼ ስልጣኔን እለቃለሁ!! ከዛ ምን ይመጣል?> ብሎ ፎክሮ ነበር። እንደባለስልጣን ሳይሆን እንደተራ መናኛ ሰው ራሱ የሚጠብቀው ነገር ቅሌት መሆኑን እየደጋገምኩ ማስታወስ ነበረብኝ። ይፎክራል እንጂ እንደማያደርገው አውቃለሁ። የስልጣን ፍቅሩ ነፍሱን እስከመገበር የሚያደርሰው ነው። ቀስ በቀስ ሀብቱን ስቀበለው። <አይኔ እያየ አትበያትም! ገድዬሽ ከሀገር እጠፋለሁ!> የሚልበት ቀን ብዙ ነበር!!

ከዚህ በኋላ ግን ሁሉም ሲኖረኝ ፣ ከህፃንነቴ ጀምሮ የኖርኩለትን ጠላቶቼን የመግደል ህልም ሳሳካ ፣ ካሰብኩት በላይ ገንዘብ እና አቅም ሲኖረኝ ………. ሁሉም ቀስ በቀስ ጣዕሙን እያጣብኝ መጣ!!! የምኖርበት ህልም አጣሁ!! ለራሴ ስል የምለው ምንም ነገር ጠፋኝ!! ለካንስ በበቀል ስካሬ ውስጥ ወጣትነቴን ሰውቼዋለሁ፣ ሴትነቴን ሰውቼዋለሁ፣ እናት የመሆን እድሌን ቀርጥፌዋለሁ ፣ ሚስት የመሆን መንገዴን ዘግቼዋለሁ ፣ ከሁሉ በላይ ግን ሰው መሆንን ገብሬ ከሰውነት ወርጃለሁ!! ………… ከዛማ በህይወቴ ከኪዳን እና በጥቂቱ ከእሙ ውጪ ምንም ነገር ፈገግ የማያስብለኝ ፣ ልኩን ከስህተቱ ያደበላለቅኩ ፣ ባህልን ከዘመናዊነት ያቀላቀልኩ ፣ ብልግናን ከጨዋነት ያጣረስኩ ፣ ምን ለምን እንደማደርግ የተወናበደብኝ ሆንኩ!! ሲረጥቡ መበስበስ ለምጄ የለ? ተበሳበስኩት!!

ሙሉሰውም ጭንቅላቱ የተዛባ እስኪመስለኝ ድረስ የሚሰራው ሁሉ የሚበላሽበት ፣ ከቀን ወደቀን የደጋፊዎቹ መወድስ እየቀነሰ የሚተቸው ሰው ቁጥር እየበዛ ጭራሹኑ አስተካክሎ የሚከውነው ነገር ጠፋው!! እዚህ ነጥብ ላይ እየፈራሁት መጥቼ ነበር። የሆነ ቀን ገድሎኝ ራሱን ሊገድል ይችላል ብዬ ማሰብ ጀምሬ ነበር። ግን ለምንድነው የማልረካው? እሱን በቁሙ ገድዬው ሌሎቹን ጨርሼ አሁንም የተሸነፍኩ ዓይነት ስሜት የሚሰማኝ ለምንድነው? ያ ሁሉ ቁስል እነርሱን ስበቀል የሚድን መስሎኝ አልነበር? ለምን አሁንም እንደድሮ ያመኛል? ያደረግኩት ክፋት እና በቀል ጥያቄዬን እንዳልመለሰ ወይም ህመሜን እንዳልፈወሰ እያወቅኩም በክፋት መቆመሬን ቀጠልኩበት።

ገንዘብ ካለ ሲደመር ስልጣኑ ያለው ሰው ካወቅኩ የማላገኘው ነገር ጥቂት መሆኑን ስረዳ የማይጣሱ ብዙ መስመሮች ጣስኩ። ከአንድ ባልደረባው ጋር በአንድ ውሳኔ ሳይግባቡ ቀርተው እራሱ ስንቴ መጥቶ የባለገበትን ቤት እንደማስፈራሪያ ተጠቅሞ የሙሉ ሰውን እጅ ጠመዘዘው። ሙሉሰው አይደለም የማይፈልገውን ውሳኔ መወሰን ቢሞት ራሱኮ ግድ አይሰጠኝም ግን ሰው መበቀል እና ክፋት ደሜ ውስጥ ያለ ነገር መሰለኝ። ሰውየው ሲባልግ በድብቅ ቀረፅኩት። የተከበረ ባለትዳር እና የልጆች አባት ስለሆነ የቀረፅኩትን ቪዲዮ ሳሳየው ሽንቱን ሱሪው ላይ ሊሸናው ምንም አልቀረውም። የሚገርመው ግን <ከዚህ በላይ ምን ሊመጣ?> ብሎ ይሆን አልገባኝም። እየመጣ መባለጉን አላቆመም!! በድብቅ ካሜራ እንደቀረፅኩት ለአንድ ሰው ትንፍሽ ቢልና አንድ ደንበኛ ባጣ በራሱ እንዲፈርድ አስጠንቅቄዋለሁ። እውነትም ለማንም ትንፍሽ ሳይል ቀርቶ ይሆን ወይም የነገራቸውም ሰዎች እንደእርሱ ሱሳቸው በልጦባቸው አላውቅም የቀረ የለም። ለምናልባቱ የምፈልጋቸውን ሰዎች የፖርን ፊልም ማስቀመጤ አልቀረም። አስፈልጎኝ የምጠቀምበት ቀን እስኪመጣ ድረስ

የሙሉ ሰውን ከቀልቡ አለመሆን ተከትሎ ህዝቡ በሱ ላይ እንዲነሳ አጋጋይ በዛ!! ጨዋ ናቸው የሚባሉት እንኳን እሱን ለመጣል ተወለካከፉ!! ጨዋታው ስላዝናናኝ ብቻ ቆሻሻቸውን እየፈለጉ ሲሸነፉ ማየት የበላይነት ስሜት ስለሚሰጠኝ ወደድኩት። ለእኔ ቀላል ጨዋታ እንደሆነው ለእነሱ አልነበረም እና ከሙሉሰው ጀርባ ነገር የምቀምረው እኔ መሆኔን ሲያውቁ ሁለት ተቃራኒ ጠላቶች አፈራሁ። የተወሰኑት ሊያጠፉኝ የሚያደቡ ሲሆኑ የተቀሩት መዝራት የፈለጉትን ክፋታቸውን እና ወጥመዳቸውን በእኔ ተከልለው መከወን የሚፈልጉ ጥቅመኞች (አጋጣሚውን ካገኙ በራሴው ወጥመድ የሚያጠምዱኝ ሴረኞች ናቸው።) ሁለቱም ወገን በአይነቁረኛ የሚፈራኝ እና የሚጠላኝ ሰውም ሆንኩ። ባሎች ለሚስቶቻቸው ስለእኔ አሙላቸው። ሚስቶች ተሰብስበው ስጋዬን በሉት። በውስጣቸው ግን እነርሱ በባላቸው ላይ የሌላቸው ስልጣን እኔ ስላለኝ ቀኑ!! ተሰብስባ በመንገሽገሽ ስሜን የምትጠራ ለብቻዋ ስትሆን ልታገኘኝ ትፈልጋለች።

እኔም ሲሰለቸኝ እሱም ሲታክተው አንድ ቀን ቤቱ ሄድኩ!! ባልገድልህም ሞተሃል ይበቃሃል ልለው ነበርኮ አካሄዴ! ከልቤ በቅቶኝ በቃህ ካሁን በኋላ የምፈልገውን አግኝቻለሁ እና በቀሌ በቅቶኛል!! ትቼሃለሁ!! ልለው ነበርኮ!!

ሞትን ራሱ በዓይኑ ያየ የሚመስል ህፃን እያባበለ ደረስኩ!! በፊት እቤቱ የነበረው ዘመዱ እኛ መረጃ ከያዝንበት በኋላ አዳሪ ትምህርት ቤት እንዲያስገባው ያስገደድኩት እኔ ነበርኩ። የህፃኑን መንሰፍሰፍ ሳይ ዘንግቼው የነበረው ያኔ ሱሪውን ዝቅ አድርጎ የመለሰው መጣብኝ። ሲያየኝ ከመደንገጡ፣ መቀበጣጠሩ፣ ውክቢያው፣ ህፃኑ እንዲሄድ ማካለቡ ……. የሆነው ነገር ያልገባኝ መስዬ ተረጋጋሁ!! ህፃኑ የጎረቤት ልጅ መሆኑን አረጋግጬ ልጁን አባብዬ ወደቤቱ መልሼ ምንም እንዳልተፈጠረ ወይም እንዳልገባኝ መሰልኩ። እስኪረጋጋ እና ድንጋጤው እስኪለቀው ጠበቅኩት። ስመጣ አስቤው የመጣሁትን ነገርኩት።

«እውነትሽን ነው? በምን አምንሻለሁ? ቪዲዮዎቹን ካልሰጠሽኝ በምን አምናለሁ? የሆነ ቀን ሀሳብሽን ብትቀይሪስ?» አለኝ

«ከቃሌ ውጪ ምንም ማስተማመኛ የለህም!! ግን ሁሉንም ነገር ወስጄብሃለሁ ከዚህ በኋላ ምን ቀረኝ ብዬ ካንተጋ አኩኩሉ እጫወታለሁ? ግን እኔስ በምን አምንሃለሁ? ማረችኝ ብለህ ልትገድለኝ ብትሞክርስ? ማረችኝ ብለህ አሁንም የሌላ ለጋ ህፃን ህይወት እንደማታበላሽ በምን አውቃለሁ?» ስለው ከተቀመጠበት ዘሎ ተነሳ!! የዚህ ቀን ነው እንደአጓጉል አድርጌ ገድዬው እጄን ለፖሊስ የሰጠሁት!!!

* * * * * * * * *

ዳዊት በሩን አልፎ ሲገባ ዋናው የጭፈራ ወለል መሃል ቆሜ ቤቱን እየቃኘሁ ነበር። ሌባ አይኖቹ እየተቁለጨለጩ ወደኋላም ወደፊትም ከማለቱ በፊት ፊቴን ማጥናት ያዘ።

«አለቃ የለብኝም ብለህ በፈለግክ ሰዓት ነውኣ የምትገባ የምትወጣው?» አልኩት ሊገድለኝ የድሮ ፍቅረኛውን እንደላከብኝ ምንም ፍንጭ እንደሌለኝ መስዬ

«የኔፍቅር አትደውይልኝም ነበር? መጥቼ እጠብቅሽ ነበርኮ» ብሎ በመገላገል እየተነፈሰ ሊያቅፈኝ ተጠጋኝ!! አንገቱን አንቄ ወደላይ አንጠለጠልኩት እና እግሩ አየር ላይ ሲወራጭ ፣ የግንባሩ ደምስር ሲፈጥ እያፀዱ የነበሩት ሁለት ሴቶች መሄድም መቆምም ተወዛግቦባቸው ሲያዩኝ ቆይተው አንዷ መጥታ እግሬ ስር ወድቃ ትለምነኝ ጀመር።
👍261
«ተነሺ ከእግሬ ላይ!!» ብዬ ጮህኩባት

«በእመቤቴ ይዤዎታለሁ!! እንደው በሚወዱት ይሁንብዎ!! እጆት ላይ ይሞታል!! ኸረ እንኳን አንጠልጥለውት በአንድ ጥፍ ባህር የሚሻገር ነፍሰ ቀጭን ሰበብ ይሆንብዎታል።»

«ተነሺ ከእግሬ ላይ አልኩኮ!! እንዲሞት አይደል እንዴ ታዲያ!» ጮህኩኝ ድጋሚ

«እኔንም እንደፈለጉ ያድርጉኝ ከፈለጉ አልነሳም!!» ብላ አንድ እግሬ ላይ ተጠመጠመች። ሌላን ሰው ለመታደግ መሬት መንበርከኳ ገረመኝ። ትንፋሽ አጥሮት ሲልሞሰሞስ እያየሁት አሰብኩ!! ንዴት ላይ ሆኜ በፍፁም የማስብ ሰው አልነበርኩምኮ!! የድሮዋ እኔ ብሆን እጄ ላይ ይህችን ደቂቃ አይቆይም! ገና ሲመጣ ዘግቼው ነበር። ሆኖልኝ ቆይቶ እንኳን ቢሆን እግሬ ስር የተደፋችውን ሴት ታግሼ ተነሺ አትነሺ ግብ ግብ አልገጥምም! ይሄኔ ገንብሬ ጥያት ነበር!! አሁን ተቀይሬያለሁ ወይም ለመቀየር እየሞከርኩ ነው! መሬቱ ላይ ለቀቅኩት!! ሴትየዋ ከእግሬ ላይ ተነሳች። እየተንከባለለ አስሎ ሲያበቃ! መሬቱ ላይ ቁጢጥ ብዬ

«ለምን? ለምን እንዳደረግከው ብቻ እውነቱን ንገረኝ!! ከዋሸኸኝ ኪዳንን ይንሳኝ እጨርስሃለሁ!!» አልኩት! ለገንዘብ ብሎ እንደማያደርገው አውቃለሁ። የገንዘብ ችግር የለበትም!!

« ግልፅ አይደል እንዴ? ስለምጠላሽ!» አለኝ እስከዛሬ አናግሮኝ በማያውቀው ጥላቻ እና ድፍረት። ደነገጥኩ። ወዲያው ከአፌ ቃል አልወጣም!!

«ልትገድለኝ እስከሞከርክ ቀን ድረስ እወድሻለሁ ስትለኝ አልነበር? እየጠላኸኝ ነው አብረኸኝ የነበርከው? ደግሞስ ምን አድርጌህ ነው እስከመግደል የምትጠላኝ?» ስለው ተነስቶ እዛው መሬቱ ላይ ተቀመጠ እና ቆመው ሲያዩን የነበሩትን ሴቶች አያቸው። እየተሯሯጡ ወደ ውስጥ ገቡ።

«ከአባቴ ቀጥሎ እንዳንቺ ያዋረደኝ ፣ ትንሽ እንደሆንኩ እንዲሰማኝ ፣ ራሴን እንድጠላ ያደረገኝ ሰው የለም። ከዛሬ ነገ ትወጂኛለሽ፣ በፍቅርሽ እፈወሳለሁ ብዬ ጠበቅኩሽ። በየቀኑ ናቅሽኝ!! ለፍቅሬ ምላሽሽ ሁሌም እንደበረዶ የቀዘቀዘ ቃላት ነው የምትወረውሪልኝ። <አንተም ወንድ ሆነህ?> ያላልሽኝን ቀን ብቆጥረው ከእጄ ጣት አይበልጥም!! ለአባቴ እንደልጅ እንደሰው ነው የከሸፍኩበት። አንቺ ግን ወንድነቴንም ነው የቀማሽኝ!! አብሬሽ ባሳለፍኩት እያንዳንዱ ቀን ትንሽ በትንሽ በራስ መተማመኔን እየሸረፍሽ ካንቺ ሌላ ሴት እንደወንድ እንኳን የማትቆጥረኝ እየመሰለኝ አብሬሽ ቆየሁ። ምክንያትሽን ሳትነግሪኝ ለወራት ስትዘጊኝ እጠብቃለሁ። ምክንያትሽን ሳትነግሪኝ ስትመለሺ እቀበልሻለሁ። ላንቺ ምንም ነኝ!! በፈለግሽ ሰዓት ሄደሽ ስትመለሺ የምታገኚኝ እቃሽ ነኝ!! እኩል ድርሻ ባለን ቤት ላይ እንኳን ፈላጭ ቆራጯ አንቺ ነሽ!! አንቺ አለቃ እኔ ባሪያሽ ነኝ!! ንገሪኝ ለመጥላት በቂ ምክንያት አይደለም?»

አልመለስኩለትም። ቁጢጥ ካልኩበት ተነሳሁ!!!! ቆሜ ምን እንደማስብ አላውቅም ግን ፈዝዣለሁ። እሱ ከአሁን አሁን ምን ታደርገኛለች ብሎ በሰቀቀን እየጠበቀኝ ነው።

«ይቅርታ!!! ይሄ ሁሉ አይገባህም ነበር። እንዲህ እንዲሰማህ ማድረጌንም አላውቅም ነበር። ስቀህ ማለፍህ ልክ የሆንኩ እንዲመስለኝ አድርጎኛል። ይቅርታ አድርግልኝ!! ከልቤ ነው አንተ ጥሩ ሰው ነህ!! ቢያንስ ለእኔ ጥሩ ሰው ነበርክ!! አይገባህም ያልኩህ የእውነቴን ነው። » አልኩት። ሞቶ መንግስተሰማያት ደርሶ ይሁን በእውኑ እዚህ ምድር ላይ ሆኖ ይሄን ከእኔ አፍ መስማቱ እያወዛገበው አይኑን ጎልጉሎ ያየኛል።

«ሙከራህን ብትደግመው የምምርህ እንዳይመስልህ!! ቤቱን ልሸጠው እፈልጋለሁ!! ህገወጥ ስራውን የምታቆም ከሆነ የእኔን ድርሻ ልሽጥልህና የቤት ኪራይ እየከፈልክ ስራበት። አይ ካልክ ግን ቤቱን ለቀህ ትወጣለህ!! እኔ ጨርሻለሁ!!» ብዬው ወጣሁ።

ከወጣሁ በኋላ ያ ስሜት ተሰማኝ!! ባዶ የሆነ ስሜት!! ጣዕም አልባ ስሜት!! የምሄድበትን ሳላውቅ እየነዳሁ ስዞር ቆይቼ አመሻሽ ላይ አባ መልከፃዲቅ ያሉበት ቤተክርስቲያን ሄድኩ!! እግራቸው ላይ ተደፍቼ ማልቀስ ፈልጌ ነው።ኮቴን ክለብ እረስቼው የለበስኩት እጁ የተጋለጠ ነገር ስለነበረ ሱቅ ገብቼ ነጠላ እና ሹራብ ደርቤ ቀጠልኩ።
በሩን አልፌ ቦታዬጋ ስደርስ አይኔ ከቆቡ ውስጥ ተጎልጉሎ ሊወጣ ደረሰ። አባ የሚቀመጡባት ጉቷቸው ላይ ተቀምጠው ጎንጥ እኔ በምቀመጥበት ቦታ እግራቸው ስር ተቀምጦ ያወራሉ። እግሬ ተወለካከፈብኝና ቆምኩ። አየኝ!! ምንም ቀን እንዳልዘጋኝ!! ልቤ በመከፋት ተኮማትራ ከእጄ ጭብጥ እንዳላሳነሳት፣ መከፋት እና ተስፋ መቁረጥ እንዳላሸከመኝ ሁሉ ፈገግ አለ

ይቀጥላል.........



ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ

ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️
👍30
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ


#ክፍል_አስራ_ሶስት

///
እንደተለመደው ከሳምንት በኃላ ወደሆቴል መጥታ እኔም ስራዬን ስሰራ አሷም ስትዝናን አምሽተን እኩለ ለሊት ላይ ተያይዘን ወደተከራየችው ሆቴል በመግባት ተቃቅፈን ተኝተን እያወራን ነው፡፡እንዴት እንደሆነ አለወቅም ወሬው ደግሞ እንደወትሮው  ፍቅር ፍቅር ሚሸት ሳይሆን ኮምጠጥ ያለ ሀገራዊ ጉዳይ ነው..፡፡ዛሬ እንኳን እሷን የሚመጥናትን ጫወታ ልጫወት ብዬ መሰለኝ በገዛ ጥያቄዬ ውስብስብ ወሬ ውስጥ እነንድንገባ መንገዱን የከፈትኩት

‹‹መቼስ ወታደር ነሽ…ለዛውም ባለትልቅ ማአረግ….የሀገሪቱን ችግር  ለማከምና ከመከራዋ እንድትወጣ ለማገዝ በደምና በላብ ዋጋ ከፍለሻል…ግን አሁን ስታስቢው መስዋዕትነቴ ባክኗል….ደሜም ያለውጤት ፈሷል ብለሽ ታስቢያለሽ፡፡?››ስል ጠየቅኳት፡፡

እስኪ ምን ሚሉት ጥያቄ ነወ….ይሄንን ጥያቄ አንድን የተከበረች ጄኔራል ስጠይቅ የሀገሪቱ ደህንንት ቢሮ ጆሮ ቢገባ የትኛው ተቃዋሚ አካል ነው አስርጎ ያስገባህ ብሎ  ቢያፍነኝ  ይፈረድበታል?
እሷ ግን ተረጋግታ መመለስ ጀመረች‹‹ፈፅሞ አላስብም…አርግጥ እኔ እንዲሆን እያሰብኩና እያለምኩ እንደነበረው የተከወነ ነገር ላይኖር ይችላል፡፡ውጤቱ ከግምቴ በጣም ዝቅ ያለ ወይንም ሙሉ በሙሉ ተቃራኒ ሊሆን ይችላል…እንደዛም ነው የሆነው፡፡ግን እኔ ነገሮችን ለማስተካከል በተሰጠኝ  ኃላፊነትና ሪሶርስ በአግባቡ በመጠቀም በቀናነት እናም በሙሉ ችሎታዬ ተንቀሳቅሼለሁ ወይ ?ብዬ ነው የምጠይቀው…መልሱ አዎ ከሆነ በቂ ነው፡

ነገሮችን ሁሉ በውጤታቸው ብቻ ከለካህ መጨረሻው ጥሩ አይሆንም… ወደፊትም አያስኬድህም፡፡
‹‹እስቲ አብራሪልኝ››
‹‹ስራዎችን ከመከወንህ በፊት ስለስራው ሞያዊ ጥናት   ታርጋለህ፡ ውጤታማ የሚደርግህን እቅድ ትነድፋለህ ፡ከዛ ወደተግባር ትገባለህ…. .በእኔ አረዳድ እቅድ በወረቀት በሰፈረው መሰረት ተግባራዊ የሚሆነው ከ50 ፐርሰንት በታች ነው..ማንኛውም እቅድ ማለቴ ነው..የጦርነት እቅድ ሲሆን ደግሞ የተለየ ይሆናል….ግን ደግሞ  እቅድ አስፈላጊና በጥንቃቄ መሰራት የሚገባው ጉዳይ ነው..ቢያንስ ነገሮችን ለመጀመር መነሻ ይሆንሀል፡: በሂደት ለሚያጋጥሙህ እዲስ ክስተቶች የሚሆን የሚሳራ ቅፅበታዊ እቅደም ለማቀድ  መነሻ  ፍንጭ ይሰጥሀል…በአጠቃላይ ለማለት የፈለኩት እንኳን እንደኛ የተወሳሰበና የተጨመላለቀ የችግር ትብታብ ያለባት ሀገር ይቅርና ባደጉት ሀገሮች የማስፈፀም ብቃት እንኳን ነገሮች እንደሀሳብ አይሄዱም..ምሳሌ አሜሪካ ኢራቅን ሰትወር  የስንት ቀን ኦፕሬሽን ብላ ገባች? ስንት አመትስ ፈጀባት…?ራሺያ ዩክሬንን ላይ ለሳምንት ብላ የጀመረችው ጦርነት  ምን ያህል ጊዜ ፈጀባት ?
ይሄ የወታደራዊ ፤ አመራሩ ችግር፤የፖለቲካኛው ችግር ፤የቦታው ነባራዊ ሁኔታ..የተፋላሚህ አቅድህን ለማበላሸት  የሚነድፈው ሌላ እቅድ…የተፋላሚህ ወዳጆች ተፅዕኖ፤የአንተ ጠላቶች በሁኔታው ለመጠቀም የሚያደርጉት ጥረት፤ ጠላትም ወዳጅም ሳይሉ ከነገሩ ገቢያቸውን ለማደለብ የሚዳክሩ ሚዲያዎች፤ነጋዴዎች፤ ደላላዎች….ምኑ ቅጡ…የአንተ ዕቅድ በእግዚያሄር ካልተዘጋጀ በስተቀር የእንዚህን ሁሉ ተዋናይ ትርምስ ከግምት አስገብቶና   በትክክል ተንብዮ የሚሰራ እቅድ ሊያዘጋጅልህ አይችልም…..እና መጀመሪያ        ይሆናል ተብሎ ተነገሮህ አንተም ያንን አምነህ ወደጦርነት ትገባለህ..እንዳልከው ላብህም ይንጠባጠባል ፤ ደምህም ይረጫል  …አካልህም እየተቦደደሰ ይበራል…..ነፍስህም ልትሰናበት ችላለች…. ውጤቱ ደግሞ ከታሰበው ተቃራኒ ወይንም በጎን የልታሰበ ሽንቁር ከፍተት እየተስገመገመ ወዳልታወቀ መዳረሻ የሚያደርስ ሊሆን ይችላል፡፡

፤የዛን ጊዜ  ልትደነግጥ ትችላለህ…ሊከፋህ ይችላል…ግን በምንም አይነት ተስፋ አትቆርጥም…ተስፋ መቆረጥ ከሁሉም ጠባሳዎችህ እንዳታገግም እና ሁለተኛ እድል እንዳሞክር እስከወዲያኛው ነው የሚያደቅህ….ሀገር ደግሞ ቢያንስ ህልውናዋ ማስጠበቅ የምትችለው ሁል ጊዜ ተስፋ በማድረግና ከነመዝረክረኩም ቢሆን ወደፊት በመጎዝ ነው፡፡በምንም አይነት ሁኔታ በሀገርህ ላይ ያለህ ተስፋ በውስጥህ እንዲፈርስ ልትፈቅድ አይገባም፡፡በተለይ በዚህ የኢንፎርሜሽን ዘመን ጦርነት በጣም የማይተነበይ እና የሸረሪት ድር አይነት የተወሳሰበ ሆኗል፡፡

ከሌላ አካል ተልኮ ተሰጥቶት እንደሚጠይቅ እንደ ችኮ ጋዜጠኛ ሙግቴን ቀጠልኩ‹‹ግን የእኛ ሀገር ዋና ችግር ምን ይመስልሻል…?ድህነታችን መሆኑን አውቃለሁ…. ቢሆንም እንደወታደር በሀገሪቱ ፍፅም ሰለም እንዳትሆን ዋናው እንቅፋት ምንድነው?፡፡

‹‹ትክክል ነህ እኮ.. በግራም ዞርክ በቀኝ ለእኛ ሀገር ዋነው ችግራችን ድህነታችን ነው፡፡፡ሚያናጥቀንም ሚያላትመንም እሱ ነው፡፡ግን ከድህታችን በመለስ ዋናው ችግር ምንድነው ካልከኝ ፅንፈኝነት ነው…ፅንፈኝነት ማለት አይነ ልቦናል ጨፍኖ በደመነፍስ ማሰብ ነው፡፡ያ ማለት በውድቅት ለሊት የቤቱን መብራት ሁሉ አጥፍቶ የጠፋብንን መርፌ ለማግኘት የመዳከር ያህል ነው፡፡ቀንቶህ መርፌውን በዳበሳ መጨበጥ ብትችል እንኳን መወጋትህና መድማትህ አይቀርም፡፡
ፅንፈኝነት የራስን ፍላጎት ጥቅምና ስሜት ብቻ  መሰረት አድርጎ ብይን መስጠት ለዛም ብይን  ደምሳሽና ጨፍላቂ ውሳኔን መውሰድ ማለት ነው፡፡

አክራሪነት በብዙ    ዘርፍ አለ....የብሄር አክራሪነት፤ የሀይማኖት አክራሪነት ፤የፆታ አክራሪነት ፤የፖለቲካ አክራሪነት…የሀገር አክራሪነት ወዘተ፡፡ፅንፈኝነት ነገሮችን ከአንድ የተቸነከረ ፖይንት ኦፍ ቪው ብቻ መመልከትና ፍርድ መስጠት ማለት ነው፡፡ወደአንዱ ፅንፍ በጣም ተለጥፈን ስንቆም ከሌላኛው ፅንፍ ያለን ርቀት በጣም ሰፊ ይሆናል…ከእይታችንም ይጠፋል፡፡
ፅንፈኞች መቼም የእኛ ነገር የመጀመሪያው ይሁን…የእኛ ነገር ይሰማ …የእኛ ነገር ይቀመስ ፤ የእኛ ነገር ይበላ….ባይ ናቸው፡፡ማመቻመች የሚባል ነገር ፈፅሞ አልፈጠረባቸውም…. የጋራ በሆነ ነገር ላይ ደግሞ የእኔ ብቻ አይሰራም…፡፡
እና እንደአንድ ወታደር የትኛውንም ሀይማኖት ተከታይ ብትሆን ችግር የለብኝም.፤የየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ብትሆን እኔን አይመለከተኝም…አህዳዊ ብትሆንም ፌዴራሊስት ብትሆንም ግድ አይሰጠኝም….ግን ሁሉም ውስጥ ሆነህ ፅንፈኛ ከሆንክ የዛን ጊዜ ችግር አለ..አንዳንድ ሰው አክራሪነት ላይ የተሳሳተ የትርጉም ስህተት ሲፈፅም አያለሁ….አንድ ሰው የራሱን ሀይማኖት ይዞ የሀይማቱን ዶግማዊና ቅኖናዊ ህግጋን ሳያፋለስ በፍፅም መሰጠትና ትኩረት ተግባራዊ በማድረጉ አክራሪ ሀይማተኛ ነው ልንለው እንችላለን…አክራሪነቱ ግን የሌላው ሀይማኖት አማኝ ላይ ድንጋይ እስካልወረወረ እና የሌላውን አማኝ ማምለኪ ቦታ ላጥቃና ላውድም እስካላለ ድረሰ በክፍትም በስህተትም ሊወሰድ አይገባም….፡፡በብሄርም ስትመጣ እንደዛው…አንድ የኦሮሞ ብሄር ተከታይ በኦሮሚኛ ቋንቋ ማውራቱ..በእየእለቱ የኦሮሞ ባላዊ ልብስ መልበሱና ገንፎና፤አንጮቴ እና ወተት የእየለት ምግቡ ማድረጉ በፍፅም ችግር የለውም…..ችግሩ በአካባቢዬ ያለው ስው ሁሉ ከአንጮቴ ውጭ ሌላ ምግብ እንዳይቀምስ ካለና በጆሮዬ ከኦሮምኛ ውጭ ሌላ ቋንቋ አንዳይሰማ በማለት  ከሌላው ብሄር ጋር ባለው መስተጋብር ችግር መፍጠር ከጀመረ ነው፡፡
👍337🔥2🥰2👏2😁1
‹‹እሱስ እውነትሽን ነው፡፡ እኔም አክራሪነትን በጣም መፀየፍ ከጀምርኩ ቆየሁ፡፡በሀይማኖት አክራሪዎች ምክንያት ሀይማኖት የሚባል ነገር እርግፍ አድርጌ ትቻለሁ…በብሄር አክራሪዎች ምክንያት ለብሄሬ ያለኝ ትርጉምና ፍላጎት ተንጠፍጥፎ ባደ ስለሆነ ብሄር አልባ አድርገውኛል፡፡፡የሀገር አክራሪዎች ደግሞ ሀገሬን ሊያሳጡኝ ጫፍ ላይ ናቸው፡፡  ›› የሚል ማብራሪያ ሰጠዋት፡፡
      
‹‹አየህ ጥሩ ገልፀኸዋል ፡፡የአክራሪዎቹን ዋና አላማ  ምንም የማይጠይቁ አባላትን ከጎናቸው ማሰለፍ እናም ከመሀከል ይሉትን ገፍተውና ተስፋ አስቆርጠው ከጫወታው ውጭ ማድረግ ነው..ከዛ ማን ይቀራል እንሱ ከነጭፍን ደጋፊዎቻው፡፡ …ተቃራኒዎቻቸውም  በተመሳሳይ የጫወታ ህግ ከነጭፍን ደጋፊዎቻቸው በዛኛው ጫፍ ይቆማሉ…..ከዛ ጦር መወራወሩና መሳሪያ መተኳኮሱ ቀላል ይሆናል…፡
.በዚሀ መሀል ሀገር ይበጠበጣል…ወታደሩ ባረባ ነገር ከአንዱ ጫፍ ወደሌላ ጫፍ እየተስፈነጠረ ሁኔታዎችን ለማስተካክል መስዋዕት መክፈሉን ይቀጥላል….ደግሞ የሚገርመው እኮ የፅንፈኞች አሰላለፍ እንደሁኔታዎች መከረባበቱ ነው፡፡አሁን በብሄራቸው መመሳሰል ምክንያት የአንድ ቡድን ማሊያ ለብሰው ለአንድ አላማ ሲፋለሙ የቆዩ  ጓደኛሞች..የጫወታው ግጥሚያ አይነት ወደሀይማኖት ሲቀየር ጭራሽ እንደማይተዋወቅ በተለያየ ቡደን ተሰለፈው እርስ በርስ ይጠዛጠዛሉ፡፡አክራሪዎች አንድ የጋራ ፀባያቸው ፀረ እኩልነት መሆናቸው ነው…በአፋቸው ቢያንበለብሉም ፈፅሞ ከሌላው ጋር እኩል መሆንን አይቀበሉም፡፡የእነሱ ሀይማኖት የሀገሪቱ የመጀመሪያ እንዲሆን ፤የእነሱ ብሄር የሀገሪቱ የበላይ እንዲሆን ወዘተ..ብቻ ነው የቀንና ሊት ህልማቸው፡፡

‹‹መፍትሄው ግን ይኖረው ይመስልሻል፡፡››

‹‹መፍሄውማ መሀከል ላይ ያሉት አንዳንተ በእነሱ ድብቅ  ሴራ በሂደቱ ተስፋ ቆርጠው ከመድረኩ እራሳቸውን ያገለሉ ወይም ጆሮቸውን ደፍነው የተኙትን ማንቃትና እነሱን ማብዛት ሲቻል ነው፡፡ ››

‹‹መንግስትስ ?›› 

‹‹እኛ ስለመንግስት የማስፈፀምና የመቆጣጠር አቅም ያለን ግንዛቤ ከእውነታው ጋር ፍፅም የተምታታ ነው።ምን አልባትም ለሺ ምናምን አመታት በነገስታት ሲገዛ የኖረ ማህበረሰብ ነገስታት ደግሞ ስልጣናቸው ከላይ የተፈቀደ የሚመርጣቸውም የሚቀባቸውም አምላክ እንደሆነ እየታመነ  ሁሉን አድራጊነትንና ሁሉን አዎቂነትን ገንዘባቸው እንደሆነ ሲወርድ ሲፈረድ  በመጣ  የክብርና የፍርሀት ስሜት ሲተዳደር የኖረ ማህበረሰብም ዛሬም መንግስት  ማለት የመጨረሻውን ወንበር የያዘው ሰውዬ እንደሆነ በደመነፍስ ማመን በሀገሪቱ ለመጣው ስኬትም ጠቅልሎ ለእሱ መስጠት ውድቀቱንም እንደዛው ጠቅልሎ  በእሱ ማሳበብ ። ሁሉን ማድረግ ይችላል ብሎ በሌለው አቅምና ችሎታ ላይ መተማመንና ተስፋ ማድረግ...ሳይፈፀም ሲገኝ ስላልቸለና አቅም አጥሮት ሳይሆን ሆነብሎ በተንኮልና በዳተኝነት  ነው ብሎ በመውሰድ መማረርና እራስን መጉዳት…ምሳሌ የምንኖርበት ከተማ ስፋቱ ምን ያህል ነው።ስንት ቀበሌ አለው?ስንት ህዝብ ይኖርበታል..?ያን ህዝብ የየእለት ደህንነት ለመጠበቅ ስንት ፓሊስ ጣቢያና ምን ያህል ፓሊስ አለ? በከተማዋ 50 የተለያየ ቦታ በአስር ደቂቃ ልዩነት አደጋ ቢደርስ እና ፓሊስ ሪፓርት ቢደረግለት ስንቱ ጋር ከምን ያህል ጊዜ በኃላ መድረስ ይችላል?የተረኛ ፓሊስ እጥረት፤የትራንስፓርት እጥረት-የተመደብት ፓሊሶች ዳተኝነት፤የአደጋዎቹ ቦታዎች ከንዑስ ፓሊስ ጣቢያዎች ያላቸው እርቀት..?
እና  ፀጥታችንን የሚጠብቀው መንግስት ነው? ደህንነታችንን እያስከበረ ያለው መንግስት ነው?አይደለም፡፡ እዚህ ላይ የመንግስት ቀጥተኛ  ሚና ኢምንት ነው።ግን ደግሞ እንደማህበረሰብ በውስጣችን ያዳበርነው መንግስትን የመፍራት…የማስፈፀም አቅሙን አጋኖ የማሰብ  ባህሪያችን እርስ በርስ እንድንከባበር አድርጎናል.. የወጡትን ህጎች የማክበር   አቅማችንም በንፅፅር ሲታይ ከፍተኛ ነው።እውነታው ግን መንግስት ህግን ለማውጣት ያለውን ብቃት ያህል እነዛ ህጎች እንዳይጣሱ ቀድሞ የመከላከል እና ሲጣሱም ተከታትሎ የመቅጣት አቅሙ ውሱን ነው።እግዚያብሄር ይመስገን ይህንን እውነት በልኩ የሚረዳ የማህበረስብ አካል ከ2 ፐርሰንት የማይበልጥ በመሆኑ መንግስት እንደሰፈር ጎረምሳ እየተኮሳተረ እና እያስፈራራ ብቻ እራሱን አስከብሮ ለረጅም ጊዜ እንዲኖር እረድቶታል፡፡
  
‹‹እና ማጠቃለያሽ ምንድነው;?››

‹‹ማጠቃለያውማ….ምን ጊዜም እራስህ በራስህ ለመጠበቅ ትጋ…ከመንግስት የምትጠብቀውን ነገር በተለይ እንደግለሰብ መንግስት ለእኔ ማድረግ አለበት ብለህ የምታስበውን ነገር  በተቻለህ መጠን ለዜሮ የተጠጋ ይሁን…ያን ጊዜ ከራስህም አልፈህ ሌሎች የእኔ የምትላቸወን ሰዎች ለመጠበቅና ለመታደግ ብቃት ይኖርሀል …በተቃራኒው መንግስት እንዲህ አደረገ...መንግስት ለምን እንዲህ አያደርግም? እያልክ በየቀኑ ስትነጫጭና ስታማርር ምትውል ከሆነ በስተመጨረሻ  የጨጓራ በሽተኛ ሆነህ ታርፈዋለህ እንጂ በህይወትህ ምንም ለውጥ አታመጣም፡›

‹አምርሮ ማማረር እኮ ወደአምርሮ መጥላት ያድጋል ...አምርሮ መጥላት ደግሞ መንግስትን ለማስወገደ እና በሌላ ለመተካት እርምጃ ለመውሰድ ይገፋፋል ፡፡››አልኳት ፈራ ተባ እያልኩ….

‹‹ችግሩ እሱ አይደል?››

‹‹እንዴት?››

‹‹በአንተ እድሜ እንኳን ስንት መንግስት ተቀየረ…?እና መንግስት በመቀያየሩ በአንተ ህይወት ላይ ያመጣው ለውጥ ምድነው..?በሀገሪቱስ..?አንዱ መንግስት ሲመጣ በዛኛው መንግስት የነበረ ሰህተትን ያስተካክል ይሆናል ግን ደግሞ ውሎ ሳያድር ተመጣጣኝ የሆነ ሌላ የራሱ ችግር ይፈጥራል..በተለይ አፍሪካ ውስጥ መንግስት መቀየር ማለት በአጠቃላይ የችግር አይነትን መቀየር ማለት ነው..››

‹‹ውይ ይብቃን የፓለቲካ መድረክ አደረግነው እኮ..››

‹‹እሺ እንደውም ደክሞኛል.ማለቴ እንቅልፌ መጥቷል እንተኛ…››

‹‹እሺ ጓደኛዬ እውነትሽን ነው እንተኛ››ተንጠራርቼ መብራቱን አጠፋሁና ልክ ከዚህ ቀደም እንደነበሩት አዳሮች አይነት አተኛኘት ተኛን፡፡

ይቀጥላል
👍48👎1🥰1
የመኖር አካፋይ የመሞት ሲሶ መንገድ መሃል........ ክፍል ሰላሳ (የመጨረሻ ክፍል)
(ሜሪ ፈለቀ)

ብዙ ጥያቄዎች ስለእርሱ እያብሰለሰልኩ አልነበር? ቅድም ተበሳጭቼበት ባገኘው የምጮህበት ሲመስለኝ አልነበር? ታዲያ ገና ሳየው እንኳን ልቆጣ የማወራውም የማስበውም ጠፍቶኝ አባን ጉልበት ስሜ እሱን እጁን ጨብጬ ተቀመጥኩ። እየመላለስኩ <ደህና ኖት> ስል ቆየሁ አባን!!

«ተገናኛችሁም አይደል? እኔ የምፈፅማት ጉዳይ አለችኝ!» ብለው ተነሱ። እሳቸው ከአጠገባችን ከራቁ ከደቂቃዎች በኋላ እንኳን ዝም ተባብለናል። የሆነ በነዚህ ባልተገናኘንባቸው ቀናት በመሃከላችን መራራቅ የተፈጠረ ዓይነት ስሜት አለው።

«ቸር ባጀሽ?» አለኝ እኔ ቀድሜ እንዳወራ ሲጠብቅ ቆይቶ! ቸር ነው የባጀሁት? እሱ ምን ሆኖ እንደዘጋኝ የሀሳብ ካብ ስከምር እና ስንድ እንቅልፍ እንቢ ብሎኝ የተሰቃየሁት ፣ እወድሻለሁ እያለ አንሶላ አብሮኝ ሲጋፈፍ የነበረው ሰው ከምድረገፅ ሊያጠፋኝ እስኪሻ አምርሮ የሚጠላኝ ሰው ሆኖ ማግኘቴ ፣ አሁን ወደዚህ እየመጣሁ በብዙ ባዶነት መዋጤ …… ይሄ ቸር ከተባለ አዎ ቸር ነው የባጀሁት!!

«መሄድ ነበረብኝ!!» አለኝ እኔ ምንም ሳልጠይቀው! ዝም አልኩ!

«አናግሪኝ እንጅ ዓለሜ?» ሲለኝ ኩርፊያዬን ትቼ <እቀፈኝ> ማለት ነበር ያሰኘኝ ደጀ ሰላም ሆንኩ እንጂ!!

«ምን ልበል? መሄድ ኖሮብኝ ነው አልከኝ አይደል? <የት? ለምን ሄድክብኝ? > የማለት መብት አለኝ? ከመሄድህ በፊት ልታሳውቀኝ እንኳን ግድ ያልሰጠህ አያገባትም ብለህ አይደል? ያስኬደህ ነገር ከእኔ በላይ ያንተን ትኩረት የሚሻ ነገር ቢሆን አይደል ሀሳብ አሳቅፈኸኝ የጠፋኸው? ዝም ከማለት ውጪ ምን አቅም አለኝ?» ስለው በጣም ስፍስፍ ባለ አስተያየት አይቶኝ ከተቀመጠበት ተነሳ

«ተነሽ እንሂድ?» አለኝ

«የት?»

«እኔእንጃ! ቁጭ ብለን የምናወጋበት ቦታ!!» ሲለኝ ለምንድነው ከተናገረው ዓረፍተ ነገር የተለየ የገባኝ? ማውጋቱንማ እያወጋን አይደል? እየነካሁሽ፣ እያቀፍኩሽ እየሳምኩሽ የማወጋሽ ቦታ እንዳለ ነው የሰማሁት። ተነሳሁ!! ደጁን ስመን ወጣን እና መኪናዬን ወዳቆምኩበት ልሄድ ስል ታክሲ ይዘን እንሂድ ሲል ለምን ብዬ አልጠየቅኩም!!

«አባጋ እንደምመጣ በምን አወቅህ?»

«ጭንቅ ጥብብ ሲልሽ የምትመጭ እዚሁ አይደል? ደሞ አርብ አይደል? አርብ አርብኮ ለወትሮም አባጋ ታዘወትሪ ነበር!»


ከዋናው መንገድ ደርሰን ከቆሙት ላዳዎች አንዱን ወደሱሉልታ ይዞን እንዲሄድ አናግሮት ከኋላ ወንበር ገባን። መንገድ ስንጀምር እጁን በትከሻዬ አሳልፎ አመልጠው ይመስል ተሽቀዳድሞ ስብስብ አድርጎ ደረቱ ላይ አደረሰኝና ጭምቅ አድርጎ አቀፈኝ።

«እኔ ላይ ሙሉ መብት አለሽ!! የልቤ አዛዡ አንቺ አይደለሽ? ያንቺን ያህል እኔ እንኳን መች በገዛ ልቤ አዝበታለሁ? አያገባሽም ብዬ አይደለም ሳልነግርሽ የጠፋሁ።» አለኝ። ካቀፈኝ በኋላ ምክንያቱን ቢነግረኝም ባይነግረኝም ግድ አልነበረኝም። ተናድጄ የነበረውን ፣ ከፍቶኝ የነበረውን ፣ ተቆጥቼ የነበረውን ፣ መጠየቅ እፈልግ የነበረውን ……… ሁሉንም ረሳሁት!! እጄን በሆዱ ላይ አሳልፌ ወገቡን አቀፍኩትና በቃ ዝም አልኩ!! እንደዚህ ታቅፌ አላውቅማ!! ደረት ከዝህች ዓለም ውጥንቅጥ መጠለያ ቤት መሆኑን አላውቅማ!! የሰው ልብ ማዘዝ እንደሚቻል አላውቅም ነበራ!! ብዙዙዙዙ ከፍቅር ጎድዬ ነበራ!! ሲጠፋብኝ ሳቄንም ሀሳቤንም ይዞብኝ የጠፋ ፣ ሲመጣልኝ ዓለምን ያስጨበጠኝ ሰው ኖሮኝ አያውቅማ!! በዚሁ ሱሉልታ አይደለም ከሀገር ይዞኝ ቢጠፋ ፣ እንዲሁ ደረቱ ላይ በክንዱ ታቅፌ ብቻ ብዙ ዓመት መሽቶ በነጋ!! ያለፈው ዘመኔ ፍቅር ያልጎበኘው ምነኛ ባዶ ነበር? ፀጉሬን ሳም አድርጎ

«እየተከተሉሽ ነበር!! …… » ብሎ ሊቀጥል ሲል

«ዝም ብለህ እቀፈኝ!! በኋላ ትነግረኛለህ!! አሁን ዝም በለኝ!!» አልኩት ከእርሱ ፍቅር ውጪ ቢያንስ ሱሉልታ እስክንደርስ መስማት የፈለግኩት ነገር የለም!! ክትትል ፣ ፀብ ፣ በቀል ፣ ሴራ ….. የት ይሄድብኛል ሲሆንብኝና ሳደርገው የኖርኩት አይደል? እንዲህ የታቀፍኩት ግን ዛሬ ብቻ ነው! እንዲህ ልቆይና የሱን የልብ ምት የእኔን የልብ ፈንጠዝያ ልስማ!! ከዛ በኋላ የሚከተሉኝ ሰዎች እንኳን አጊንተው ቢገድሉኝ ታቅፌ ነበር ፣ የእናትን ሞት በሚያስረሳ እቅፍ ታቅፌ ነበር፣ የበረደው ልብ በሚያሞቅ እቅፍ ታቅፌ ነበር፣ መኖር ጀምሬ ነበር።


«እሽ» ብሎ ባላቀፈኝ እጁም ደርቦ አቅፎኝ አንዴ ጨመቅ አንዴ ላላ ሲያደርገኝ ፣ አሁንም አሁንም ፀጉሬን ሲስመኝ ደረስን። ልጁን መንገድ እንደሚያሻግር አባት እጄን ይዞኝ የገባው ሪዞርት ውስጥ ካሉት ትንንሽ ጎጆ ቤት መሳይ አንደኛው ጋር ገብተን ፊት ለፊት ለፊት ለፊት ተቀመጥን። ጎጆ ቤትዋ ውስጥ እኛ ከተቀመጥንበት ጠረጴዛ በተጨማሪ ሌላ አንድ ጠረጴዛ ቢኖርም ሰው የለውም ነበር እና እኔና እሱ ብቻ ነበርን። አስተናጋጁ የሚታዘዘውን ጨራርሶ እንዲሄድልን አጣድፈን አዘን ሸኘነው። መብት አለሽ ተብዬ የለ? ሁለቱንም እጄን ጠረጴዛው ላይ ዘርግቼ እንዲይዘኝ ሰጠሁት። በሁለቱም እጆቹ ያዘኝ።

«እሺ አሁን ንገረኝ!!» አልኩት በስስት የሚያዩኝን አይኖቹን(መሰለኝ) እያየሁት

«ከወየት ልጀምር?»

«እኔ እንጃ!! ማነህ? ምንም ሳይቀር ስላንተ ማወቅ እፈልጋለሁ!» ስለው ዓይኖቹ ውስጥ መከፋት ነገር ያየሁ መሰለኝ ወይም ፍርሃት እኔንጃ

«እሽ! ምንም ሳላስተርፍ አወጋሻለሁ!! ግና የቱ ነው ማን መሆኔን የሚገልጥልሽ? ያለፈ ህይወቴ? የመጣሁበት ብሄር ጎሳዬ? አባት አያት ቅድመአያቴ? እምነቴ? የእስከዛሬ በጎ ምግባሬ ወይስ ሀጥያቴ? ወይሳ አሁን የሆንኩት እኔ? በየትኛው ነው አንት ይህ ነህ ብለሽ ምትቀበይኝ?» አለኝ ያለፈው ህይወት አድካሚ እንደነበር በሚያሳብቅ መልኩ።

«ሁሉም መሰለኝ!! የሁሉም ድምር መሰለኝ አንተን አንተ የሚያደርግህ!! ሁሉንም ልወቀው!!»

«ደግ!! ከማን ጎሳ መገኘቴ ፍቅርሽን ያሳሳብኛል?» አለኝ ሲሆን አይቼው እንደማላውቅ ሽንፍ ብሎ በልምምጥ

«የእነሱ ወገን አትሁን እንጂ ….. » ብዬ የአባቴን ገዳዮች ጎሳ ከመጥራቴ መልሱን ፊቱ ላይ አገኘሁት!! ማድረጌን ሳላውቀው እጄን ቀማሁት። ልቤ ድው ድው ማለቱን ያቆመ መሰለኝ። ከዛች የተረገመች ቀን ጀምሮ እድሜዬን ሙሉ ስጠላቸው ኖሪያለሁ። ያለፉትን ወራት ግን ልቤን የሞላው የሱ ፍቅር ጥላቻዬን ከድኖት ክፋትን እየሸሸሁ ፣ በቀልን እና ጥላቻን ከልቤ እያስወጣሁ ሌላ ሰው ልሆን እየሞከርኩ አልነበር? ለምን እንዲህ ተሰማኝ ታዲያ? የሱ ፍቅር ሌላው ላይ ያለኝን ጥላቻ እንጂ ማጥፋት የሚችለው እሱ የምጠላውን ሆኖ ሲመጣ ፍቅሩ አያሻግረኝ ይሆን? ዝም ብዬ መሬት መሬቱን ሳይ አስተናጋጁ የታዘዘውን ይዞ መጥቶ ጠረጴዛው ላይ መዋከብ ጀመረ። ቀና ብዬ አየሁት። እያየኝ ነው። ዓይኔን በዓይኑ ሲይዘው በሚለምን አስተያየት አየኝ!!

«እሺ አንድ ነገር ንገረኝ? እኔጋ መስራት መጀመርህ የእነሱ ወገን ከመሆንህ ጋር ተያያዥነት አለው?»

«የለውም ዓለሜ!!» አለኝ እንደተጨነቀ እያስታወቀበት።
👍391👏1
«አባቴንኮ የገደሉብኝ ያንተ ወገኖች ናቸው፤ ማን ያውቃል ወይ አጎትህ ወይ አባትህም ሊሆን ይችላል፤ እናቴን መሳሪያ ይዘው የደፈሩብኝኮ እነዛው ያንተ ወገኞች ናቸው፤ ልጅነቴን ፣ወጣትነቴን ፣ ጉልምስናዬን ያመሳቀሉብኝኮ ያንተ ወገኖች ናቸው ፤ አምርሬ ስጠላቸው እና ላጠፋቸው ስመኝኮ ነው የኖርኩት። በህይወቴ አንድ ጥሩ ነገር ቢከሰት ፣ አንዴ ፍቅርን ባገኝ ፣ አንዴ ብሸነፍ …… እሱም የእነሱ ወገን ይሁን?» እያልኩት ውስጤኮ ቁጭት ነው የሞላው ቃላቶቹ ከአፌ ሲወጡ ግን እንባዬን አስከትለው ሀዘን የተሸከሙ ነበሩ።

«አንዴ ሁሉን ስሚና ፍረጅኝ!! ሰምተሽ አሻፈረኝ ከአሁን ፍቅሬ ያለፈ በደሌ ይበልጣል ካልሽ ምን ማድረግ ይቻለኛል? ልብሽ ያለሽን አድርጊ!! እ? እ ዓለሜ?» ከፊት ለፊቴ ተነስቶ አጠገቤ ወንበር አድርጎ ተቀመጠ። እንዳያቅፈኝም እንዳይነካኝም የቸገረው መሰለ። እንዳየው በዓይኖቼ ዓይኖቼን ያሳድዳል።

«እሺ ንገረኝ! ሁሉንም ልስማህ!! የእነሱ ወገን መሆንህን ግን የትኛው ታሪክ ይቀይረዋል?»

«ፍቅር! ፍቅር ይቀይረዋል! ፍቅር ጎሳ ብሄር ሀገር የለውምኮ ዓለሜ? እኔስ አስቤ እና አቅጄ በፍቅርሽ የወደቅኩ ይመስልሻል? ላንች እስከተንንበረከኩባት ሰዓት ድረስ እኔምኮ ያንቺን ጎሳ እንገሸገሸው ነበር። ሁሉም ቤትኮ እሳት አለ ዓለሜ!? ከጥላቻዬ አስበልጬ ወድጄሽ ነው! ከቂሜ አስበልጬ ወድጄሽ ነው፣ ፍቅርሽ ልቤ ሲሞላ መበደሌን ይቅር ብዬ ነውይ!» ብሎ ጀርባዬ ላይ አንድ እጁን ደገፍ አደረገ።

«የአባትን ሞት ያህል በደል አልተበደልክማ! የእናትን መደፈር ያህል ቂም አልያዝክማ! እድሜህን ሁሉ የቀማህ ጥላቻ አልጠላህማ!!» አልኩት ማልቀሴን ሳላቆም! ከተቀመጠበት ተነስቶ እንደገና ወደነበረበት ተመልሶ

«ህም!!» አለ እና በረዥሙ ተንፍሶ ቀጠለ። « እኮ የእኔ ህመም ይተናነስ እንደው ሰምተሽ ፍረጅኛ!! አብይ ህፃን ሳለሁ ነው የሞተው!! እንደመጎርመስ ብዬ ድምጤ የሻከረ ጊዜ እምይ ታማ ካልጋ ዋለች። ህመሟ እንዲህ ነው ሳይባል ወሰድ መለስ እያደረጋት እድሜ ቆጠርን!! እኔ እና ትልቅ ወንድሜ ነበርን እርሻውኑም ከብቱንም ብለን እምዬን የምናኖራት። ትልቄ እንደታላቅነቱ ሀላፊነት አለብኝ ብሎ ትምህርቱን ተወው!! እኔ በቀለሙ ትንሽ ፈጠን ያልኩ ስለነበርኩ እኔን ከትምህርት እንዳልጎድል አገደኝ። 10 ክፍል ስማር ሳለሁ አንድ እለት ተማሪ ቤት እየተማርን ሳለ ከተማው በጩኸት ሰከረ። በላይ በላያችን እየተረጋገጥን ብቅ ስንል ከተማው ይንቦለቦላል። ያልነደደ ቤት ያለ አይመስልም ነበር። ሁሉም የራሱን ቤተኞች ደህንነት ሊያጣራ ሲሮጥ መደሚጤሰው ከተማ ገባ። የምማርበትን ደብተር በትኜ ስበር ወደቤት ሄድኩ። በመንገዴ ከከተማው ግማሽ የሚያህለው ቤት እየነደደ መሆኑን ሳይ አልጋ ላይ የዋለች እምዬን እሳት በላብኝ ብዬ ነፍሴ ስትጨነቅ ደረስኩ። ቤታችን ሲነድ ደረስኩ። እምይ በደረቷ ስትሳብ ከበሩ ደርሳ ነበር።» ብሎኝ ፊቱ በሀዘን ተውጦ ከንፈሩን ነከሰ።

« እሳት የጀመረው ቀሚሷን አፈር በትኜ አጥፍቼ እሷን በክንዴ ላይ አቅፌ ከጎረቤት የነበረ እሳት ያላገኘው የወንድሟ ቤት አስቀምጫት ለወንድሜ ሚስት ሀደራ ብዬ እንዲህ ካለ ግርግር መሃል አይጠፋም እና አንዳች ነገር እንዳይሆንብኝ ብዬ ወንድሜን ፍለጋ ወጣሁ። ሰፈርተኛው እሳቱ የባሰ እንዳይዛመት ሊያጠፋ ደፋ ቀና ይላል። ደመኞቻችን እጃቸው የደረሰውን ታህል ቤት አንድደው ፣ የደረሰው እህል ላይ እሳት ለቀውበት ወደገበያ መሃል መግባታቸውን ከመንገድ ስሰማ በአሳላጭ ቅያስ በርሬ ደረስኩ። (ክብድ ያለው ትንፋሽ ግንባሩን አኮሳትሮ ተነፈሰ እና ቀጠለ) ያንች ዘመዶች ገበያው ዳር የተፋለሟቸውን የከተሜውን ወንዶች ሬሳ አጋድመው ሲጨፍሩ ደረስኩ። ትልቄ ለስራ ከለበሰው ቡት ጫማውጋር በእጁ የአብዬን ጠብመንጃ እንደያዘ ተዘርግቷል።» ሲለኝ ሳላስበው

«ሞተ?» አልኩኝ

«እህ!! (ጭንቅላቱን ወደላይ እና ወደታች እየነቀነቀ) እንደዋዛ ድፍት ብሎ ሞተ። አድብተው እንደሌባ አጥቅተውን እንደጀግና እየጨፈሩ መሪያቸውን ትከሻቸው ላይ ተሸክመው በሽለላ እያወደሱት ያጋደሙትን ሬሳ ሲዞሩ ቆይተው ከተማውን ለቀው ወጡ!! ድምፃቸው ከጆሮዬ ብዙ ጊዜ ዋለ - የወንድ ዋርካ የጀግና አድባር
የአምሳል አባት ባለዝናር …… » እሱ ድሮ በልጅነቴ ለአባቴ ሲገጠም የማውቀውን ግጥም በቃሉ ወረደልኝ። እኔ ግን የአምሳል አባት ከሚለው በኋላ ያለውን አልሰማሁትም!! ሰውነቴ ቀዘቀዘ። ሁሉም ቤት እሳት አለ ያለኝ ይሄን ነበር? ታዲያ ይሄን እረስቶ ወዶኝ ነው? ሊበቀለኝ ፈልጎ እንጂ!!!

«እኔጋ መቀጠርህ ከቀዬህ ጋር የሚያያይዘው ነገር የለም አላልከኝም?» አልኩት ሳላስበው

«የሚያያይዘው የለም!! ያ ሰው አባትሽ መሆኑን ያወቅሁት ራሱ አንቺጋ ከገባሁ ከወራት በኋላ ነው!!» አለኝ ረጋ እንዳለ። ዝም አልኩኝ!!

«ታምኚኛለሽ? እንድዋሽሽ የሚያደርግ አንዳች ምክንያት የለኝም! አለመንገር እችል አልነበር? የምፈልገው በቀል ከነበር እጄ ላይ ነበርሽኮ ዓለሜ!! በብዙ መንገድ ላደርገው እችል ነበር። ለእነደሳለኝ መረጃውን እስኪያገኝ ነው ያልተበቀለኝ ብለሽ ታስቢ ከሆነ ልንገርሽ!! ሁሉንም አውቃለሁ!! ባንክ ያስቀመጥሽውን ኮፒ ፣ እሙጋ ያስቀመጥሽውን ፣ ሴትየዋጋ ያለውን!! እቤትሽ መታጠቢያ ቤት መስታወት ጀርባ ያለ ድብቅ ካዝናሽ ውስጥ ያሉ መረጃዎችሽን፣ ኮዱን ልነግርሽ እችላለሁ። የቀረኝ አለ? ሁሉን ደርሼበታለሁ!!! በቀል ከነበር ዓላማዬ እጄ ላይ ነበርሽ!! ታምኚኛለሽ? እርግጥ ነው ብዙ ጥላቻ እና ቂም ነበረኝ ግን የበቀል ሰው አልነበርኩም!!» ሲለኝ የማስበው ተምታቶብኝ የነገረኝን ትርጉም ልሰጠው እታገላለሁ!! ይሄን ሁሉ ካወቀ ምንድነበር የሚሰራው በሬ ላይ? ያሰብኩትን ያወቀ ይመስል

«አላውቅም!! ለምን እንደቆየሁ አላውቅም!! መች በፍቅር እንዳየሁሽ አላውቅም!! ብቻ አንቺን መጠበቁን ወደድኩት!! የዚያን ቀን መሄዴ ነው ስልሽ ከልቤ ነበር!! ወረቀት አኑሬልሽ ልሄድ ነበር። እውነታውን ፅፌ አኑሬልሽ ልሄድ ነበር። እንደማይባል እንደማይባል ብለሽ ታች ላይ አድርሰሽ ሰድበሽኝ ወጣሽ!! ስዘገጃጅ ፖሊስ በሩን አንኳክቶ መመታትሽን ነገረኝ!! ልቤ ሁለት ሆነ። ከሆስፒታል እስክትወጪ ታግሼ እቤትሽ ስትገቢ ጠብቄ ልሂድ ብዬ ጠበቅኩ!! ስትመጭ ጭራሽ ሌላ ሰው ነበርሽና ትቼሽ መሄድ አልቻልኩም!!» (የዛን ቀን ያለውን ቀን እኔ እየከተለኝ የነበረ መኪና አስተውዬ <የሆነ ሰው እየተከተለኝ ነው!! የተለየ ነገር አስተውለሃል? በንቃት ተከታተልልኝ> ልለው ስወጣ ነበር ስራዬን መልቀቄ ነው ያለኝ። ምን እንደዛ እንዳናደደኝም አላውቅም!! እሱ ክብሩ ከሚነካ ሞቱ እንደሆነ አውቃለሁ ግን ተናገርኩት!! ስወጣ <ጥርግ በል! ያንተ ቢጤ 10 አመጣለሁ> ማለቴን አስታውሳለሁ።
👍22
«እሺ ታዲያ እንዴት ከእነርሱ ጋር መስራት ጀመርክ?» አልኩት የነገሩን ጅማሬ ውል እየፈለግኩ

«ተዚያማ ትልቄ ሲሞት እምዬን ማስተዳደር በኔ ላይ ወደቀ። ያሸተ እህላችንን በእሳት ስላጋዩት ለከርሞ የሚቀመስ አልነበረም!! ቀዬው በጠኔ ደቀቀ። ይህኔ እምዬን ለወንድሟ አደራ ብዬ ወታደር ቤት ገባሁ!! ከዛ በምልክላቸው ፍራንክ እንደሆነው እንደሆነው አድርገው ከራረሙ።ወታደር ቤት ዓመታት ከቆየሁ ኋላ ወደቀዬ ተመልሼ መኖሪያዬን ቀለስኩ!! ምሽት አገባሁ ልጄን ወለድኩ!! ሚሽቴ ከ9 አቁማ የነበረውን የቀለም ትምህርት የመቀጠል እና በትምህርቷ ከፍ ያለ ቦታ የመድረስ ምኞቷ ትልቅ ስለነበር ከተጋባን ኋላ አስተምራት ነበር። የ12 ክፍል ትምህርቷን ስትጨርስ ሸጋ ውጤት አመጣች!! አዲስአበባ ዩንቨርስቲ ለትምህርት ተመደበች እና የ6 ዓመት ጨቅላ ልጃችንን ትታ መምጣት ግድ ሆነ!! ገና ከወራት ግን የልጇ ናፍቆት አቅቷት ተመልሳ መጣች። እሷ ከህልሟ አጓጉል ከምትሆን ምናባቱ ያገኘሁትን ሰርቼ እኖራለሁ ብዬ ልጄን ምሽቴን ይዤ አዲስአበባ ገባሁ!! ስራውንም ሳላማርጥ እየሰራሁ ባጀሁና ትንሽ ስደላደል እምዬንም አመጣኋት እኔጋ!! እንዳያልፍ የለም መቼም እንዴትም እንዴትም እሷ ተመረቀች። ይሄኔ እሷ ናት ይሄን ስራ በሰው አገኘሁልህ ብላ ደሳለኝጋ ያገናኘችኝ። እሷ ተመርቃ ከፍ ያለ ስራ ይዛ ከፍ ካሉ ሰዎች ጋር መዋል ስትጀምር ከእኔጋ መኖሩን እየተጠየፈችው መጣች። የምለብሰው አይጥማት ፣ አካሄዴ አይጥማት ፣ የማወራው አይጥማት …… ትምህርት ሚሽቴን ቀየራት ….. ትምህርት ሚሽቴን ነጠቀኝ!!» አለ ከደረቱ ቀና እንደማለት ብሎ በቁጭት ነገር የሆነ መፅሃፍ ትረካ ነገር በሬድዮ እየሰማሁ ያለሁ ነው እየመሰለኝ ያለው።


«ኋላማ ትዳራችን እንደማይሆን ሆነ። አቶ ደሳለኝ ጋር በጥበቃ ሰርቼ የማገኛት ገንዘብ ለሚስቴ ከራሷ ደመወዝ ጋር ተደምሮላትም የሚበቃትን ኑሮ አላኖር አለኝ። ኋላ ላይ አቶ ደሳለኝ በሷ ጥቆማ የግሉ ጠባቂ አደረገኝ። መድሃንያለም በሚያውቀው የዚህን ጊዜ ሁለቱ የሆነ ነገር ይኑራቸው የማውቀው የለኝም!! አይኔ ስር የሚሰሩትን ቆሻሻ ስራ አያለሁ!! ንፁህ ሰው አግተው ሲዝናኑ አያለሁ!! ቤቴን አቆም ብዬ አንገቴን ደፋሁ። ሰውየው <ልዩ ጠባቂዎቼ > የሚላቸው አሉት!! ስራው ጥበቃ አይደለም! ቆሻሻ ስራዎችን መስራት ነው!! የሚፈልገውን ሰው ከመሰለል እስከማገት ፣ መረጃ መስረቅ ፣ …… እነርሱን ተቀላቀል ሲለኝ አሻፈረኝ አልኩ። ሚሽቴ ብዙ ብር የሚያስገኝልኝን ስራ እንቢ ማለቴን ደሳለኝ እንደነገራት ነግራኝ ስትቆጣ የዚያኔ እምነቴ ሙሉ ስለነበር አልጠረጠርኳትም!! ብሩ ቢያስፈልጋት ነው ብዬ ስራውን ተቀበልኩ!! እሷን ካስደሰተልኝ እና በሷ ፊት ሞገስ ከሆነኝ ምናባቱ ብዬ ገባሁ!! ብዙ ወዳጅ አፈራሁ!! ስለከተማ ሰው ብዙ አወቅኩ!! እንዲያ ህሊናዬን አቆሽሼ ብዙ ብር ባመጣላትም ሚሽቴን አላቆየልኝም!! ፍታኝ አለችኝ!! በግድ ይዤ ላቆያት አልችል ለቀቅኳት።»

«ትወዳት ነበር!»

«ሚሽቴ አይደለች እንዴ? ቤቴ እኮ ናት የልጄ እናት! እንዴት አልወዳት?» አለኝ እንደመቆጣት ብሎ

«አይ እንዴት ሆነልህ ብዬ ነው! ባለፈው ሳያችሁ የሌላ ሴት ሚስት ሆና ምንም የመሰለህ አትመስልም ነበር።»

«ያልፋልኮ! ያልፋል! ቅናቱም ፣ ህመሙም ፣ እህህ ማለቱም ያልፋል!»

«እና ደሳለኝን ካገባችው በኋላ እሷን እያየህ ስራ እዛው እንዴት ቀጠልክ?»

«እኔና እሷ ከተፋታን ኋላ ትንሽ ቆይቶ እምይ በጠና ታመመችብኝና ለህክምና 10 ዓመት ብሰራ የማላገኘው ፍራንክ ተጠየቅሁ!! አቶ ደሳለኝ ብሩን ሊያበድረኝ እና በምትኩ ለ3 ዓመት የታዘዝኩትን ልሰራ ያቀረበልኝን ሀሳብ ለማለፍ ምርጫዬ የእምዬ ህይወት ነበርና ፈርሜ ገባሁበት!! እምዬን አዳንኩበት እኔ የማልወጣው ሀጥያት ውስጥ በየቀኑ ሰመጥኩ እንጅ!! ከዚያማ የልጄ እናት የአለቃዬ ሚስት ሆና መጣች። ትቼ አልሄድ ቃሌ ፣ ፊርማዬ ….. አልቀመጥ ሽንፈት ፣ ቅናት ፣ መከዳት ፣ መታለል ፣ መዋረድ አንገበገበኝ። ያልፋል አልኩሽ አይደል? አለፈ። እሷን ወይ አብራኝ እያለች አላውቃት ይሆን ወይ ከትምህርቱ በኋላ ተቀይራ : ጭራሽ የማላውቃት ሰይጣን ሴት መሆኗን አለቃዬ ስትሆን አወቅኩ። ለእኔ እንዲያ ብትሆንም ለልጄ ወደር የሌላት እናት ናት!! ልጄ በቋሚነት እኔጋ ብትሆንም ከአርብ እስከእሁድ እሷጋ ትሆናለች። አብረሽኝ ሁኝ ብትላት ልጄ እኔን መረጠች» አለ ኮራ ብሎ በፈገግታ ቀጥሎ

«አንቺጋ ስቀጠር ያገናኘን ሰውዬ ያንቺ ወዳጅ ቢሆንም በድብቅ የእነርሱ ወዳጅ ነው!! ያው ዘበኝነት ገብቼ የፈለጉትን መረጃ እንዳመጣ ነበር። ልጄ የታመመች ጊዜ » ብሎ ጊዜውን በማስታወስ ነገር ፍዝዝ አለ። «ልክ ያሁን ያህል አስታውሳለሁ። በረንዳው ላይ ተቀምጠሽ!

«ቤተሰብ ነኝ ብዬ ከቀበሌ የሆነ ወረቀት እናሰራ እና የእኔ ከሆናት የኔን ኩላሊት እሰጣታለሁ!» ስትይ ነው ለመጀመሪያ ጊዜ እንደስራዬ ሳይሆን እንደሰው ያየሁሽ!! የዚያኔ ነው ለምን እንደሆን እንጃ ስላንች ማወቅ ናፈቅኩ። እናቷ ያንች ኩላሊት መስማማቱን ስነግራት አይሆንም አለች። ፈጣሪ ደግ ነው ሌላ ሰው ተገኘና ልጄ ዳነችልኝ! በሰው በሰው ሳጠራ ማን እንደሆንሽ ደረስኩበት። ስራዬን ልልቀቅ ካልኩሽ በኋላ ለእነርሱም ሄጄ ሌላ ስራ እንዲቀይሩልኝ ጠየቅኳቸው። በእኔ ምትክ እንዲገባ አናግረሽው የነበረውን ሰውዬ እነርሱ ናቸው የላኩልሽ!! የሰው ተፈጥሮ ያልፈጠረበት የሰይጣን ቁራጭ አረመኔ ነው!! ምንም እንኳን የምጠላው ጎሳ ፣የወንድሜ ገዳዮች ልጅ ብትሆኝም ለልጄ ስትይ አካልሽን ልትሰጭኝ ስስት አልነበረብሽም እና ለዚያ አውሬ አሳልፌ ልሰጥሽ አልሆነልኝም!! መልሼ ሀሳቤን አንስቻለሁ እሰራለሁ በቃ ብዬ ተመለስሁ!!» ብሎ ነግሮኝ እንደጨረሰ ነገር ዝም አለ።
👍232
«ከዚያስ!»

«ከዚያማ ምን የማታውቂው ቀረ?»

«ይቀራል እንጂ! መች ነው የወደድከኝ? የተመታሁ ቀንኮ ግን ትተኸኝ ልትሄድ ነበር ለነሱ ትተኸኝ!»

«መች እንደወደድኩሽ ምኑን አውቄው? ስገቢ ስትወጭ ስትገለምጭ ስትሰድቢኝ!! አንዳንዴ ነገረ ስራሽ አፍሽ እንጅ የከፋ ልብሽ ደግ መሆኑን ሲነግረኝ አላውቅም!! እነርሱ የሚፈልጉትን መረጃ ሁላ አግኝቼ ለእነርሱ አሳልፌ ልሰጥሽ አቃተኝ!! ጥላሽን የማታምኝ ሴት እኔን ግን ከነጭርሱ አለመጠርጠርሽ አሳዘነኝ!! እንጃ ካስታወሽ የሆነ ቀን ለሊት ገብተሽ በር ስከፍትልሽ <አንተ ግን ደስተኛ ነህ?> አልሽኝ።»
ብሎ ፈገግ አለ። አስታወስኩት።

ትንሽም ቢሆን ደስታዬ የነበረው ከእሙጋ በማሳልፈው ጊዜ የነበረ ጊዜ እሷ የማያገባት ነገር የመቆስቆስ ሱሷ አላስቀምጥ ብሏት ለአምስተኛ ጊዜ የታሰረች ቀን ነው። (እኔ እስር ቤት ለ6 ዓመት እያለሁ እሷ ሁለቴ ገብታ ወጥታለች። ስትገባ አብረን ጊቢውን እናምሳለን። ከጋዜጠኝነቷ ባሻግር ታቱ መስራት በልምድ ተምራለች። እስር ቤት ውስጥ እንኳን ዘመናዊ ንቅሳት ልትነቀስ ፀጉሯን ከሁለት ጉንጉን የዘለለ የማትሰራ የገጠር ልጅ ሁላ ሳትቀር በጋዜጠኛ ምላሷ አዋክባ አሳምና ትነቅሳታለች። የጀርባዬን እና የቂጤን ንቅሳት ግማሹን መጀመሪያ የገባች ጊዜ የተቀረውን ቀለም ያልደረሰው ቦታ እየፈለገች ሁለተኛ ስትመለስ የነቀሰችኝ እሷ ናት።) የዛን ቀን መታሰሯን ሰምቼ የበረደው ልቤን ይዤ ስባዝን አምሽቼ ስገባ ጎንጥ ከእንቅልፉ ነቅቶ በር ከፈተልኝ። በረንዳው ጠርዝ ላይ ተቀምጬ እያየሁት በህይወቱ ምንም ግድ የሚሰጠው አይመስልም ነበር።

«አንተ ግን ደስተኛ ነህ?» አልኩት በመገረም እያየሁት! እንደገመትኩትም ቁልል ብሎ

«ፈጣሪ ይመስገን!!» አለኝ

«ምን ማለት ነው ፈጣሪ ይመስገን? መልስኮ አልሰጠኸኝም!! ነህ አይደለህም? ነው ጥያቄው ! ነኝ ወይም አይደለሁም! ነው መልሱ»

«ምን ለየው!! ፈጣሪ ይመስገን ማለቴ ደስተኛ በመሆኔም አይደል?» ብሎ አሁንም መልስ ያልሆነ መልስ ይመልስልኛል።

«አንተ ግን መቼ ነው ቀጥተኛ ወሬ የምታወራው? ምናለ አሁን ነኝ ወይ አይደለሁም ብትል!! ምንህ ይቀነሳል?»

«እሽ ካሻዎት! አዎን ደስተኛ ነኝ!! ምነው? እርሶ ደስተኛ አይደሉም እንዴ?» አለኝ መልሴ የጨነቀው አይመስልም። እኔ ግን ውስጤ መከፋቴ ሞልቶ ስለነበር መተንፈስ ለማልፈልገው ሰው ገነፈለብኝ።

«ደስታ ምን እንደሚመስል ስለማላውቅ ደስ ቢለኝም ማወቄን እንጃ!! አላውቅም!! ደስታ ማለት መሳቅ ከሆነ ስቄኮ አውቃለሁ። በህይወት ውስጥ ምን ያህሉን ፐርሰንት ደስተኛ ስትሆን ነው ደስተኛ ነኝ የሚባለው? እኔእንጃ! አላውቅም ደስተኛ ሆኜ ማወቄን! ሰው የሚፈልገው ሁሉ ኖሮት እንዴት ደስታ አይኖረውም አይደል?» አልኩት እና ጎንጥ መሆኑን ሳስብ ትቼው ገባሁ!!

«የዚህን ቀን አንጀቴን አላወስሽው!!» አለኝ አሁን ሳቅ ብሎ! «ከዛ ወዲህ ያለውን አላውቅም በጣም ብዙውን ቀን ታናድጅኛለሽ ለራሴ በቃ እተዋለሁ ይህን ስራ እላለሁ መልሼ ግን ያቅተኛል። የልጄ እናት በደንብ ስለምታውቀኝ ጠረጠረች። እየለገመ ነው እንጂ ይህን ያህል ጊዜ ምንም ፍንጭ ሳያገኝ ቀርቶ አይደለም ብላ ሰው ልትቀይር ነበር። ከዛ በላይ ምክንያት ደርድሬ ብቆይም አንች ፍቅሬን የምታይበት ልብ አልነበረሽም እና ደጅሽ መክረሜ ትርጉም አጣብኝ ለዛ ነው ልሄድ የነበር!! እንደው ጥሎብሽ ስታይኝ ትበሰጫለሽኮ!! ምን በድዬ ነው ግን እንዲያ የምትጠይኝ?»

«ኸረ አልጠላህም!! አላውቅም!! እሙ ስለምትወጂው ነው እንደዛ የምትሆኝው ነው ያለችኝ!» ስለው አይኑን አፍጥጦ ሲያየኝ አብራራሁ «ከፀብ ውጪ የምታውቂው ፍቅር ስለሌለ ፍቅርሽን የምትገልጪበት መንገድ ነው የምትናደጂውና የምትቆጭው አለችኝ! እሷ ናት ያለችኝ!» አልኩኝ!! ሳቅ ብሎ ዝም ተባብለን እንደቆየን እህሉ ሳንነካው መቀዝቀዙን አየን!! ሁለታችንም የመብላት ፍላጎት አልነበረንም!! እኔ የምበላው መዓት ነገር አቀብሎኝ እንዴት ነው እህል የማስብ የነበረው። ልክ እንደቅድሙ አጠገቤ መጥቶ ተቀመጠ እና አገጬን ከፍ አድርጎ አይኖቼን እያየኝ።

«መድሃንያለም ምስክሬ ነው! የደበቅኩሽ የለኝም!! ከፍቅርሽ ውጪ አንቺጋ ያኖረኝ ምንም ሰበብ የለም!! አሁን ሁሉን አውቀሻል!! አልሻህም እሄዳለሁ ካልሽኝም በግዴ የእኔ አላደርግሽም!! ብትተይኝም ከአፌ የሚወጣ ሚስጥር የለም!! በልጄ እምልልሻለሁ!! እ? ዓለሜ? ፍቅሬ ከጥላቻሽ ከበለጠ ንገሪኝ!! እሽ በይኝና የኔ ሁኝ በደልሽን በፍቅር እንድትረሽ አደርግሻለሁ!!» ሲለኝ ለተወሰነ ደቂቃ የእነሱ ወገን እንደሆነ ረስቼው እንደነበር አስታወስኩ። አባቴ ከወንድሙ ገዳዮች አንዱ ወይም አዛዡ እንደነበር አውቆ እንዴት ቻለበት ማፍቀሩን!

«ስትጠፋብኝ ስላንተ መረጃ እንዲያቀብሉኝ አድርጌ ነበርኮ!!» አልኩት የተጠየቅኩት ሌላ የምመልሰው ሌላ እንደሆነ እየገባኝ

« እየተከተሉሽ ነበር። ከኪዳን ጋር ከተማ ስትገቡ እንዴት እንደሆነ መረጃ ደርሷቸው ነበር። ኪዳን በሰላም እንዲወጣ እኔ ጣልቃ መግባት ነበረብኝ!! (ፍጥጥ ብዬ ሳየው) ምንም አልሆንኩም!! » አለኝ እጁን ከአገጬ አውርዶ

«ምንድነው ያደረግከው?» አልኩት

«ብዙም አይደል! ዋናው ኪዳን መውጣቱ ነበር ያንቺ እዳው ገብስ ነው!!» አለኝ

«ይሁን ንገረኝ ምንድነው ያደረግከው?» ብዬ ጮህኩ

«ከረፈደ ነው መኪና እንደተመደበባችሁ የሰማሁት!! ምንም ማድረግ የምችለው ስላልነበር መኪናውን ተጋጨሁት!! ምንም አልሆንኩም!! ማንም አልተጎዳም!! ትራፊክ መጥቶ ስንጨቃጨቅ እናንተ ተሰውራችኋል። እኔን ተከትለው ሊደርሱብሽ ስለሚችሉ ካንቺ አካባቢ መጥፋት ነበረብኝ! ለጊዜው የሚያቆሙ ይመስለኛል። ሌላ መላ እስኪያገኙ!! አንቺን መከተል ካላቆመች ለልጄ ማንነቷን እንደምነግራት ነግሪያታለሁ!! መረጃዎች እንዳሉኝ ስለምታውቅ ለጊዜው አትሞክረውም!! ስጋታቸው አሁን ለምርጫው የሆነ ነገር ታደርጊያለሽ ብለው ፈርተው ነው!! የምታደርጊውን እስክታስቢ ፋታ ይኖርሻል!! (ትንሽ ፋታ ወስዶ)መች ነው ግን አንቺ የምታምኝኝ? ምን ባደርግ ነው ትቶኝ ይሄዳል ወይ ይከዳኛል ብለሽ የምታስቢውን የምታቆሚው?» አለኝ

«አላውቅም!! እኔ እንዲህ የምወደው ነገር ኖሮኝ አያውቅም! እንዲህ የተሸነፍኩለት ነገር ኖሮኝ አያውቅም!! እንዲህ የተንሰፈሰፍኩለት ሰው ኖሮኝ አያውቅም!! ባጣው የምሞት መስሎ የተሰማኝ ሰው ኖሮኝ አያውቅም!! የምወደውን ስጠብቅ የኖርኩት በመጠራጠር እና በጉልበት ነው!! ማመን እንዴት እንደሆነ አላውቅማ!!» አልኩት አስቤ የተናገርኩት አልነበረም!!

ፈገግ ብሎ ፊቱን አዞረ እና መልሶ በተመስጦ ሲያየኝ ቆይቶ ሁለቱን እጆቹን በአንገቴ ዙሪያ ልኮ አንገቴን እንደመደገፍ ፣ ከአገጬ ቀና እንደማድረግ አድርጎ ከንፈሩን ከንፈሬ ላይ አሳረፈው። ስሞኝ እጆቹ እዛው እንዳሉ ከመልሴ በኋላ መልሶ እንደሚስመኝ ነገር

«ያ ማለት ምን ማለት ነው? አለሽልኝ ማለት ነው? እ? ንገሪኛ?» ከንፈሩ ከንፈሬን ከነካው በኃላ እንኳን ዘሩን ያለሁበትን የማላስታውስበት ስካር ውስጥ ከቶኝ ነው የሚጠይቀኝ? በጭንቅላቴ ንቅናቄ አዎ!! አልኩት!! ከንፈሩን እቦታው መለሰው!!

......... አሁን ጨርሰናል!!..........
👍7512🥰10
#እህቴ_ባትሆኚ_አገባሽ_ነበረ
:
:
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
:
:
#ክፍል_አስራ_አራት

/////

እለተ እሁድ ነው፡፡ረፋድ ላይ ቁርሴን ከበላሁ በኃላ ወደአልገዬ ተመልሼ ልጄ የላከችልኝን የእናቷን ማስታወሻ በተመስጦ እያነበብኩ ነው፡፡ይሄ ታሪክ የአፈላነት ጊዜ ታሪካችን ነው፡፡ትኩስ ወጣት ሆነን የኖርነው፡፡ወጣትነት ውስጥ የሚንፎለፎል ኃይል አለ።"ልክ የኒዩክሌር ኃይል አይነት።ወደማብራት ኃይል ተቀይሮ ልማትን ሚያሳልጥ...ወደአውዳሚ ቦንብ ተቀይሮ   ለጦርነት ውሎ ከተማን የሚያፈርስ  ወጣትነት ከተራራ የሚገዝፍ ነገሮችን የማድረግ ጉጉት እና   ሳይታክቱ የመሞከር ትጋት ..ቢወድቁ በፍጥነት ተነስቶ የመቆም ፅናት፡፡ አዎ  ከሰው ልጅ የዕድሜ እርከኖች ጎልደን ኤጅ የሚባለው ነው ወጣትነት፡፡ ህፃንነትና ታዳጊነት ከኃላው ትቶ ጎልማሳነትና አዛውንትነትን ከፊቱ አስቀምጦ  ከህይወት ዘንግ የመሀል አንጓ ላይ ያለ በዕንቁ  ያሸበረበቀ ጌጥ ነው።

ወጣትነት ውበት በመጨረሻው እንጥፍጣፊ አቅሙ የሚጎመራበት ስሜት ክላይማክሱን ገጭቶ የሚንፎለልበት የአበባነት እድሜ ነው።የፍቅር  ኮንሰርት ቢዘጋጅ የዳንሱን መድረክ የሚሞላው ወጣት ነው...የጦርነት ነጋሪት ቢመታ ለመስዋዕትነት ግር ብሎ የጦር ካንፑን የሚያጨናንቀው ወጣት ነው።አብዬት አንስቶ ከተማውን በድንጋይ አጥሮ አስፓልቱን በጎማ ጭስ የሚያጥነው ወጣት ነው....ለድጋፍ ሰልፍ ቲሸርትና ኬፕ ገድግዶ ጎዳናውን በመፈክርና  በባንዲራ የሚያጣብበውም ያው ወጣት ነው። በቀደድለት ቦይ የሚፈስ ፤ባሳዩት መንገድ የሚነጉድ ወጣት ነው።ቤተ እምነቱ የሚሻማው ቤተመንግስቱም የሚፈራው ያው ወጣት ነው...፡፡ ወጣት ሆነህ ጥበብ  ቀድሞ ከበራልህ ቤተእምነትም ሆነ ቤተመንግስት  አያታልሉህም....፡፡ፓለቲከኛው በስሜትህ ጢባጢብ አይጫወትብህም ...፡፡አዎ የነቃህ ወጣት ከሆንክ  ለእሱ ወደስልጣን ማማ መስፈንጠሪያ እስፕሪንጉ ለመሆን በምንም አይነት ሁኔታ ፍቃደኛ ልትሆን አትችልም" ግን ወጣትነት በብዙ ችኮላ ፤ፋታ በማይሰጥ ጉጉት፤ ስር ባልሰደደ ዕውቀትና ልምድ የሚጓዝ በመሆኑ ከስህተት ሊፀዳ አይችልም፡፡እርግጥ ሙሉ የሰው ልጅ ከስህተት ጋር የእድሜ ልክ ትስስር አለው…ወጣትነት ላይ ግን  ይለያል..እኔም እንደአብዛኛው ሰው ህይወቴን ያጨመላለቅኩት በዚህ የወጣትነት ዕድሜዬ በሰራሁት ስህተት ነው፡፡ውይ እስቲ መዘበራረቁን

ገታ አድርጌ እጄ ላይ አንከርፍፌ የያዝኩትን ከሪች ማስታወሻ ፎቶ ተንስቶ በልጄ አማካይነት በቴሌግራም የተላከልኝን ቀጣይ ታሪክ ላንብብላችሁ፡፡

ሰኔ 5 2008 ዓ.ም
11 ኛ ክፍል ሆነን ነው፡፡ማታ 11 ሰዓት ሆኖ ከትምህርት ቤት ከገባን በኃላ በምን ሰዓት በየት እንደሄደ ሳላውቅ እዬብ ከቤት ወጥቶ ጠፋ..ሰፈር ዞር ዞር ብዬ ብፈልገው ላገኘው አልቻልኩም.ግራ ገባኝ…ማታ እራት ሰአት ላይም ተመልሶ አልመጣም.. እነእማዬ ሲጠይቁኝ ጓዳኛዬ ጋ አብረን እናጠናለን ሲል ሰምቼለሁ ብዬ ዋሸሁ…የቤቱ ሰው ሁሉ ከተኛ በኃላ አምስት ሰዓት አካባቢ የክፍላችን መስኮት ከፈትኩለት.ዘሎ ገባ፡፡

‹‹እስከአሁን አልተኛሽም እንዴ?››

‹አፈር ብላ…ዝም ብለህ ከቤት ወጥተህ እስከእዚህን ሰዓት ድረስ ትቆያለህ?››

‹‹የእኔ ውድ እህት …አሳስብኩሽ እንዴ ..?

ድንገተኛ በረከት አጋጥሞኝ ነው፡፡››

‹‹የምን በረከት ነው?››

‹‹ባክሽ ሶፊያ ጋር ነበርኩ››
አቤት የደነገጥኩት
ድንጋጤ‹‹ሶፊያ የት? .ለምን?.ከእሷ ጋር ምን አባህ ትሰራለህ?››

ተንሰረዘረኩበት ፤አዎ ሶፊያን በደንብ አውቃታለሁ...አረ እንደውም. የክፍላችን ልጅና ለእኔም ጓደኛዬ ነች..የተበሳጨሁበት ጉዳይ ግን ወደጎን ነው፡፡ሶፊያ እዬብዬን በጣም እንደምትወደው አውቃለሁ፡፡.ማለት እንደምታፈቅረው አውቃለሁ….ብዙ ጊዜ ደጋግማ ‹ወንድምሽን አፈቅረዋለሁ› …ብላ ነግራኝ ፊት ነስቻታለሁ፡፡እንደዛ ስትለኝ የማቀርብላት ምክንያት ‹ወንድሜ ጎበዝ ተማሪ ነው..ያለጊዜው ፍቅር ምናምን እያልሽ እንድታዘናጊው አልፈልግም› የሚል ነበር››ዋናው ምክንያቴ ግን ያ አልነበረም…እዬብን ፍቅረኛም ሆነ ጓደኛ በሚል የብእር ስም አንድ ሴት መሀከላችን ገብታ እንድትሻማኝ አልፈልግም፡፡

‹‹እረጋ በይ እቤቷ ነበርን››አለኝ.በሚያበሳጭ የድምፅ ቃና..

‹ለመሆኑ እስከዚህን ሰአት እቤቷ ጎረምሳ ስታቆይ እቤተሰቦቾ ምንም አይሏትም?››

‹‹አታስቢ የእኔ እህት… ብቻዋን ነበረች››

‹‹ብቻዋን?››

‹‹አዎ ምነው ደነገጥሽ…ገጠር ሄደዋል… ብቻዋን ስለምታድር ነው የጠራቺኝ››
‹‹እና ምነው ብቻዋን ጥለኸት መጣህ ..የሆነ ነገር ቢያስደነግጣትስ…?አብረሀት አታድርም ነበር?››
‹‹እንኳን አድሬ ላመሸሁትም ሞቼልሻለሁ…አንቺ ጓደኛሽ እንዳንቺ መሰለችሽ.. አስጮኸችኝ እኮ››

‹እስጮኸችኝ ማለት…?መታህ ነው
አስደንግጣህ?››

‹‹አይ አንቺ ልጅ በቀላሉ አይገባሽም…ወሲብ ፈፀምን ….ወሲብ እንደዚህ እንደሚጥም ዛሬ በእሷ አወቅኩ፡፡››

‹ወሲብ .ወይኔ እቴትዬ…ወይ እግዚያብሄር ድረስ..ከተቀመጥኩበት አልጋ ተነሳሁ .እንባዬ አራት መስመር ሰርቶ በጉንጮቼ ላይ መፍሰስ ጀመረ…ወለሉ ላይ ተዘርፍጬ መሬቱን አሰስኩት..እዬቤ ያላሰበው ዱብ እዳ ነው የገጠመው...በጣም ግራ ገባውም በጣምም ደነገጠ.

‹‹አንዴ ምን ሆነሻል.?አረ ደምፅሽን ቀንሺ.እነቴቴ አንዲሰሙ ተፈልጊያለሽ እንዴ?›

‹‹አንተ እንዴት እንዲህ ትሰራለህ…?ምን ነክቶህ ነው?››

‹‹ምን ችግር አለው ?ይሄ እኮ ማንም ወጣት የሚሰራው ኖርማል ነገር ነው›

‹አይደለም እኔስ ወጣት አይደለሁ ለምን ሳልሰራሁም…?ለምን ቆይ?
‹‹እሱን እግዲህ እራስሽን መጠየቅ ነው››

‹‹አይደለም..በሽታውስ እንዴት እንዲህ እንዝላል ትሆናለህ.?.በዛ ላይ ብታረግዝብህስ…?ምን አባህ ልታደርግ ነው…ደግሞ ቤተክረስቲያን ይሄን ሁሉ ዘመን የተመላለስከው ለዚህ ነው፡፡ይሄ እኮ ዝሙት ነው..››

‹‹አረ በፈጠረሽ..እኔ ፀፀት እንዲሰማኝ ለማድረግ የሚያስቸልሽን አንድም ምክንያት እኮ አልቀረሽም..እኔ እኮ አስቤበት አልነበረም አሷ ጋር የሄድኩት..ድንገት ነው ሳናስበው ወደወሲብ የገባነው….ጥሩነቱ ግን እሷ ሁሉንም አዘጋጅታ ነበር የጠበቀችኝ.››

‹‹ሁሉንም ማለት?››

‹ኮንደም ነበራት..ልታረግዝ አትችልም አትፍሪ... በሽታውም እንደዛው…››

‹‹እሷማ አዎ እንደዛ ታደርጋለች …ልምድ ያላት ሸርሙጣ ነች፡፡እሺ የእግዚያብሄር ቃልን መጣሱስ? ዝሙቱስ?›
‹እሱን አንግዲህ አንዴ ተሳሳትኩ ወደኃላ መልሼ አልውጠው…ማድረግ የምችለው ንሰሀ መግባት ነው…እሱን አስብበታለሁ…አሁን እንተኛ ደክሞኛል አለኝና ልብሱን ፊቴ አወላልቆ ከውስጥ ገባና ከጭቅጭቄ ለማምለጥም ጭምር መሰለኝ ጥቅልል ብሎ ተኛ፡፡
‹‹እኔማ ከሻርሙጣ ጋር አብሬ አልተኛም›› አልኩና አልጋ ልብሱን ከላዩ ገፍፌው ትራሴን ወሰድኩና ምንጣፍን ወለሉ ላይ ዘርግቼ ተኛሁ…ተነስቶ እንዲለምነኝ ፤ጉንጬን፤ ግንባሬን እየሳመ ይቅርታ እንዲጠየቀኝ…እቅፍ አድርጎ ፀጉሬን እያሻሸ ሁለተኛ አልመለስበትም ብሎ በስሜ እየማለ ቃል እንዲገባልኝ ፈልጌ ነበር….እሱ እቴ ዝም አለኝ….ደረቅ ወለል ላይ ብገላበጥ..እህህ ብል ምንም ጭራሽ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ውስጥ ገብቶ ማንኮራፋት ጀመረ..
👍37