#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ጊዜው የበጋ ወቅት እንደመሆኑ መጠን የሁዌልቫ አየር እጅግ ማራኪ ነበር።
ሁዌልቫ ሶራ ከወር በፊት ብርዳማው የክረምት ወቅት
ከመውጣቱ አስቀድሞ ካፖርቱን ከጥጥ የተሰራ የአንገት መጎናፀፊያውንና የሱፍ ቆቡን እያደረገ ወደ “ኢስላእ ክርስቲናእ"
ወደብ በመሄድ የአሳ ማጥመጃ ጀልባዎች በአትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ
ሲንሳፈፉ ዲካ አልባውንም የአትላንቲክ ውቅያኖስ አድማስ... ማየት
የመኪናውን ሙቀት መስጫ እንደከፈተም ከኮሎምበስ ሐውልት ስር ከተደረደሩትና የፍቅር አላማቸውን ከሚቀጩት ስፔናውያን ጎን
አቁሞ እያሸጋገረ የጠፋው ነገር እንዳለ ሁሉ አትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ ማፍጠጥ ያዘወትር ነበር።
የአገሩን አፈር የአገሩን ባንዲራ ከኮለምበስ ሐውልት ሙዚየም ውስጥ አይቷል። ያ ጠንካራው የውሀ ጀግና ከዘመናት
በፊት ዘግኖ ያመጣውን የአገሩን አፈር ከግዙፉ ሐውልት ስር ካለው
ሙዚየም መስታዋት ውስጥ ተመልክቷል: አፈሩ ከወርቅና እንቁ
በላይ እንደሆነ ሁሉ አፍሶ ቢያሸተው ዘግኖ ቢጨብጠው እንደስኳር
ቢቅመው ተመኝቷል: ግን አልቻለም:: በመካከላቸው ጠንካራ መስታዋት አለ: የአፈሩን ጠረን ባፍንጫው ማሽተት እንኳን
ተመኝቶ አልተሳካለትም።
የአገሩ ባንዲራ የአቢሲኒያ ባንዲራ" ይላል አንጂ ቀለሙ ለቋል: ትክ ብሎ ሲመለከተው ግን ያ የቀስተ ዳመና ቀለም ያ ከህፃንነቱ ጀምሮ “የማሪያም መቀነት ለኔ..." እያለ ጮቤ የረገጠለት
ትምህርት ሲማር እንደገባ በጮርቃ አስተሳሰቡ በእንቦቀቅላነቱ.
አንጋጦ እያየ ያዜመለት አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለማት ባንዲራው ታየው ያኔ እጆቹን ዘርግቶ እንባው ከአይኖቹ እየፈሰሰ መስታዋቱ
ላይ ተደፋ።
“መለያዬ መታወቂያዬ...
የጥቁርነቴ አርማ... የነፃነቴ
ምልክት” ብሎ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለም ያለው ባንዲራ ንፋሱ “ጧ" እያደረገው "ሰማዩ ላይ ሲውለበለብ
ታየውና ሆድ ባሰው ባይተዋርነት ተሰማው ማንነቱን ያጣ ሆነ
ብቸኝነት ስለት ጥፍሩን አሹሎ መላ አካሉን ቧጠጠው: ውስጡ
ደማ በብሶቱ ህሊናው ደረቀ ስሩ እንደተቆረጠ እፅዋት ሲጠወልግ ሲወይብ እራሱን ተመለከተው: ስለዚህ ብሶቱን በእንባው ለውሶ
ወፍራሙ እንባው እንደጎርፍ የተሰበረ ልቡን እየሸረሸረው ወደ ውጭ ተደፋ። ማንነቱን ከአጣ ቆይቷል። ከርሱ ቢሞላም ህሊናው ግን
በፍርፋሪ ማንነት ሊጠግብ አልቻለም: እየሄደ ይቆማል እየሰራ ይቃዣል ሲስቅ እንባው ከየት መጣ ሳይባል በአይኖቹ ይሞላል...
“ማነህ?” ሲሉት እውነት ማን ነኝ! የማንነቴስ መለያ ምንድን ነው? ለምንስ ዓላማ እኖራለሁ? ቅዠቴስ ለምን በረከተ? እውን የምበላውን የሚያፈራ አፈር የለኝም? የሚለበስ በታሪኩ
የሚያኮራ ባንዲራስ የለኝም..." ይልና በሃዘን ይንዘፈዘፋል።
ከወር በፊትም ያጋጠመው ይኸው ነው: የማንነት ረሃቡ
አይሎ ብቸኝነት በዚያ ስለታም አካፋው ህሊናውን እየሰቀሰቀ አንጎሉን ሲያቦካበት ህመሙ እየለበለበ ሲያቃጥለው ልቡ ሲደማ መስታዋቱ ላይ ተደፍቶ ኮሎምበስ ከዘመናት በፊት ያመጣውን
የአገሩን አፈርና ባንዲራ ተማፀነ።
“ምነው አምላኬ መግባባትንና መቻቻሉን ነፈግኸን። ምነው
የርሃብተኞች ምሳሌ አደረግኸን...” ሳግ ተናነቀው እንባው እንደ
ዶፍ ዝናብ ወረደ ንፍጡ ተዝረከረከ፡ በዚህ አጋጣሚ የሆነ ሰው ከተደፋበት ቀስ አድርጎ ቀና አደረገው: ሶራ ከሙዚየሙ ክፍል
ወጥቶ የአትላንቲክ ውቅያኖስ የማዕበል ነፋስ አካሉን ሲዳስሰው
የተለያየ ሃሳብ ተፈራረቀበት።
ከተደፋበት ያቃናው ግን ማን እንደሆነ ለምንስ ከሐዘኑ እንዳናጠበው ለምን አብሮት
እንደሚራመድ አሰበ
ነፋሱ እየበረታበት ሀሊናው እየተስተካከለ ማሰብ ሲጀምር የያዘውን ሰው
ማንነት ለማየት ሞከረ።
ወፍራም ሰማያዊ ሹራብ
የፈረንሳዮችን ቡትስ ጫማ
የተጫማች ካፖርት ለብሳ ፀጉሯን በሱፍ ኮፍያ ብትሸፍንም በእንቢታ ያፈነገጡ ፀጉሮችዋ ፊቷ ላይ ብን ብን እያሉ በሚያምረው ጠይም የፊት ቅርጿ ላይ የሚራወጡ፣ በግራ ትከሻው በኩል ወገቡን በእጆችዋ አቅፋው ተመለከተ።
ጡቷ ብብቱን ሊነካካው
ተገርሞ ትክ ብሉ አያት: ፈገግ አለችና አይኗን ሰበር አደረገች። በእርግጥ እርዳታዋ ራሱን መቆጣር እስከሚችልበት ድረስ በመሆኑ እስኪረጋጋ ጠበቀችው። ከዚያ
“ግራሊያስ” አላት በስፓንሽ አመሰግናለሁ ለማለት።
“ዴናዳ...” አለች ምንም አይደል ለማለት። ለቀቅ አድርጋው! አሁን የተረጋጋህ ይመስለኛል። ስለዚህ ብሄድ ይከፋሃል?" አለችው።
በዚህ ግላዊ ህይወት ጥልቅ መሰረት ያለው ፎቅ እየሰራ ባለበት ዓለም አፓርታማው ውስጥ የሚኖረውን ኗሪ በግል ህይወቱ ገብተው
“ለምን ሳቅህ?... እያሉ መጠየቅ የግል ነፃነቱን እንደመዳፈር ስለሚቆጠር መርዳትና መተባበር የሚችሉትን ፈፅሞ ሌላውን ጣጣ ለባለቤቱ ትቶ ዘወር ማለት ተገቢ በመሆኑ ልጅቷ ካለምንም ጥያቄ፡-
“ደህና ሁን” ብላው ስትሄድ ከወገቡ በፊት እጥፍ ብሎ
አጆቹን ዘርግቶ እጅዋን ያዛት: በግርምታ ዘወር ብላ አየችው አያት እሱም: ወዲያው ሃፍረት ተሰማው ወንጀለኝነት ስሜት አደረበት።የያዛት እጁ እጅዋን አለቀቀም። እሷም ለማስለቀቅ አልሞከረችም።
እጁ ግን ሲንቀጠቀጥ ይሰማታል። ስሜቱም ሲለዋወጥ ተመልክታዋለች። ስለዚህ ልታፈጥበት ልትገስፀው አልፈለገችም:
“አዝናለሁ" አላት ፈገግ
ለማለት ቢሞክርም ቅንድቡ
እየተንቀጠቀጠ እያሳጣው።
“ለምን?” አለችው በፅሞና።
“ትንሽ እንድትቆይ መጠየቅ በመፈልጌ..." አላት ቀስ ብሎ እየተጠጋ።
“ማዘን አያስፈልግህም! ቶሎ መሄድ ስላሰብኝ ግን አሁኑኑ መሄድ አለብኝ።" እጆቹን ኪሱ ከተተና አድራሻውን የያዘውን ካርድ
እየሰጣት “ብትችይ ደውይልኝ አላት በትህትና።
“አዝናለሁ” ትከሻዋን ሽቅብ ሰበቅ አድርጋ “ወደ አፍሪካ
መሄድ ስለምፈልግ ጊዜ የለኝም።''
“አፍሪካ...” ከነበረበት ቅዠት ሙሉ ለሙሉ ነቃ።
“አፍሪካ የት?" አላት ፊቱ ላይ ደስታ እየታዩ፡
“አያቴ አገር... ኢትዮጲያ” ስትለው አለከለከ: ድንጋጤ
አይሉት ደስታ ላብ እስኪያሰምጠው ድረስ ተሸበረ:
“ኢትዮጵያ!... ኢትዮጵያ... ኦ! አምላኬ እኔም ኢትዮጵያዊ ነኝ። የሃዘኔም ጦስ ናፍቆት ነው..." ሲል ልጅቷ አይኖችዋን አጥብ
ተመለከተችውና
“ኮንችት”
“ምን?”
“ፔሶ ቤኒ ኮንቺት እባላለሁ። ነገ በአስር ሰዓት እዚሁ እንገናኝ አለችውና ሄደች።
በግርምታ ከአይኑ እስክትጠፋ ተመለከታት።
“…አያቴ አገር ኢትዮጲያ... ያለችው እንደገና ጆሮው
ላይ አቃጨለበት ደስ አለው። ስለ ኢትዮጵያ አብሮት የሚያወራ
አግኝቷል፡ ከጉጉቱ የተነሳ ግን ነገ ራቀበት: ያን ሩቁን ነገ እንግዳውን ነገ. መጠበቅ ግን ግዴታው ነበር።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሶራ መኪናው ውስጥ ሆኖ በሃሣብ ፈረስ ከርቀት ደረቱን እንደ ጎረምሳ ገልብጦ ከሚመጣው የአትላንቲክ ውቅያኖስ ማዕበል ይገባና አብሮ ብቅ ጥልቅ እያለ እየሰጠመ እየተንሳፈፈ ወደ ዳር
ይመጣና ካለው የሲሚንቶ ግንብ ጋር እየተጋጨ እንደ ጥይት ጮሆ.አረፋ ሲደፍቅ... እራሱን እያዬ መሪው ላይ ተደፍቶ ሲጨነቅ ተመልሶ ደግሞ አይኖቹን ውቅያኖሱ ላይ ተክሎ በሃሣብ ለረጅም ጊዜ ሲንቦራጨቅ በምናቡ አለም መግቢያ ጠፍቶት ሲዛክር ቆዬ:
ቶዮታ ኮሮላ መኪና ቀስ እያለች አልፋ ክፍቱ የመኪና
ማቆሚያ ላይ ተስተካክላ ቆመችና ሞተሯ ጠፋ: ለተወሰነ ጊዜ ፀጥታው እንደገና ሰፈነ። ከዚያ የአስር ሰዓት ደወል ተሰማ።
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ጊዜው የበጋ ወቅት እንደመሆኑ መጠን የሁዌልቫ አየር እጅግ ማራኪ ነበር።
ሁዌልቫ ሶራ ከወር በፊት ብርዳማው የክረምት ወቅት
ከመውጣቱ አስቀድሞ ካፖርቱን ከጥጥ የተሰራ የአንገት መጎናፀፊያውንና የሱፍ ቆቡን እያደረገ ወደ “ኢስላእ ክርስቲናእ"
ወደብ በመሄድ የአሳ ማጥመጃ ጀልባዎች በአትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ
ሲንሳፈፉ ዲካ አልባውንም የአትላንቲክ ውቅያኖስ አድማስ... ማየት
የመኪናውን ሙቀት መስጫ እንደከፈተም ከኮሎምበስ ሐውልት ስር ከተደረደሩትና የፍቅር አላማቸውን ከሚቀጩት ስፔናውያን ጎን
አቁሞ እያሸጋገረ የጠፋው ነገር እንዳለ ሁሉ አትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ ማፍጠጥ ያዘወትር ነበር።
የአገሩን አፈር የአገሩን ባንዲራ ከኮለምበስ ሐውልት ሙዚየም ውስጥ አይቷል። ያ ጠንካራው የውሀ ጀግና ከዘመናት
በፊት ዘግኖ ያመጣውን የአገሩን አፈር ከግዙፉ ሐውልት ስር ካለው
ሙዚየም መስታዋት ውስጥ ተመልክቷል: አፈሩ ከወርቅና እንቁ
በላይ እንደሆነ ሁሉ አፍሶ ቢያሸተው ዘግኖ ቢጨብጠው እንደስኳር
ቢቅመው ተመኝቷል: ግን አልቻለም:: በመካከላቸው ጠንካራ መስታዋት አለ: የአፈሩን ጠረን ባፍንጫው ማሽተት እንኳን
ተመኝቶ አልተሳካለትም።
የአገሩ ባንዲራ የአቢሲኒያ ባንዲራ" ይላል አንጂ ቀለሙ ለቋል: ትክ ብሎ ሲመለከተው ግን ያ የቀስተ ዳመና ቀለም ያ ከህፃንነቱ ጀምሮ “የማሪያም መቀነት ለኔ..." እያለ ጮቤ የረገጠለት
ትምህርት ሲማር እንደገባ በጮርቃ አስተሳሰቡ በእንቦቀቅላነቱ.
አንጋጦ እያየ ያዜመለት አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለማት ባንዲራው ታየው ያኔ እጆቹን ዘርግቶ እንባው ከአይኖቹ እየፈሰሰ መስታዋቱ
ላይ ተደፋ።
“መለያዬ መታወቂያዬ...
የጥቁርነቴ አርማ... የነፃነቴ
ምልክት” ብሎ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለም ያለው ባንዲራ ንፋሱ “ጧ" እያደረገው "ሰማዩ ላይ ሲውለበለብ
ታየውና ሆድ ባሰው ባይተዋርነት ተሰማው ማንነቱን ያጣ ሆነ
ብቸኝነት ስለት ጥፍሩን አሹሎ መላ አካሉን ቧጠጠው: ውስጡ
ደማ በብሶቱ ህሊናው ደረቀ ስሩ እንደተቆረጠ እፅዋት ሲጠወልግ ሲወይብ እራሱን ተመለከተው: ስለዚህ ብሶቱን በእንባው ለውሶ
ወፍራሙ እንባው እንደጎርፍ የተሰበረ ልቡን እየሸረሸረው ወደ ውጭ ተደፋ። ማንነቱን ከአጣ ቆይቷል። ከርሱ ቢሞላም ህሊናው ግን
በፍርፋሪ ማንነት ሊጠግብ አልቻለም: እየሄደ ይቆማል እየሰራ ይቃዣል ሲስቅ እንባው ከየት መጣ ሳይባል በአይኖቹ ይሞላል...
“ማነህ?” ሲሉት እውነት ማን ነኝ! የማንነቴስ መለያ ምንድን ነው? ለምንስ ዓላማ እኖራለሁ? ቅዠቴስ ለምን በረከተ? እውን የምበላውን የሚያፈራ አፈር የለኝም? የሚለበስ በታሪኩ
የሚያኮራ ባንዲራስ የለኝም..." ይልና በሃዘን ይንዘፈዘፋል።
ከወር በፊትም ያጋጠመው ይኸው ነው: የማንነት ረሃቡ
አይሎ ብቸኝነት በዚያ ስለታም አካፋው ህሊናውን እየሰቀሰቀ አንጎሉን ሲያቦካበት ህመሙ እየለበለበ ሲያቃጥለው ልቡ ሲደማ መስታዋቱ ላይ ተደፍቶ ኮሎምበስ ከዘመናት በፊት ያመጣውን
የአገሩን አፈርና ባንዲራ ተማፀነ።
“ምነው አምላኬ መግባባትንና መቻቻሉን ነፈግኸን። ምነው
የርሃብተኞች ምሳሌ አደረግኸን...” ሳግ ተናነቀው እንባው እንደ
ዶፍ ዝናብ ወረደ ንፍጡ ተዝረከረከ፡ በዚህ አጋጣሚ የሆነ ሰው ከተደፋበት ቀስ አድርጎ ቀና አደረገው: ሶራ ከሙዚየሙ ክፍል
ወጥቶ የአትላንቲክ ውቅያኖስ የማዕበል ነፋስ አካሉን ሲዳስሰው
የተለያየ ሃሳብ ተፈራረቀበት።
ከተደፋበት ያቃናው ግን ማን እንደሆነ ለምንስ ከሐዘኑ እንዳናጠበው ለምን አብሮት
እንደሚራመድ አሰበ
ነፋሱ እየበረታበት ሀሊናው እየተስተካከለ ማሰብ ሲጀምር የያዘውን ሰው
ማንነት ለማየት ሞከረ።
ወፍራም ሰማያዊ ሹራብ
የፈረንሳዮችን ቡትስ ጫማ
የተጫማች ካፖርት ለብሳ ፀጉሯን በሱፍ ኮፍያ ብትሸፍንም በእንቢታ ያፈነገጡ ፀጉሮችዋ ፊቷ ላይ ብን ብን እያሉ በሚያምረው ጠይም የፊት ቅርጿ ላይ የሚራወጡ፣ በግራ ትከሻው በኩል ወገቡን በእጆችዋ አቅፋው ተመለከተ።
ጡቷ ብብቱን ሊነካካው
ተገርሞ ትክ ብሉ አያት: ፈገግ አለችና አይኗን ሰበር አደረገች። በእርግጥ እርዳታዋ ራሱን መቆጣር እስከሚችልበት ድረስ በመሆኑ እስኪረጋጋ ጠበቀችው። ከዚያ
“ግራሊያስ” አላት በስፓንሽ አመሰግናለሁ ለማለት።
“ዴናዳ...” አለች ምንም አይደል ለማለት። ለቀቅ አድርጋው! አሁን የተረጋጋህ ይመስለኛል። ስለዚህ ብሄድ ይከፋሃል?" አለችው።
በዚህ ግላዊ ህይወት ጥልቅ መሰረት ያለው ፎቅ እየሰራ ባለበት ዓለም አፓርታማው ውስጥ የሚኖረውን ኗሪ በግል ህይወቱ ገብተው
“ለምን ሳቅህ?... እያሉ መጠየቅ የግል ነፃነቱን እንደመዳፈር ስለሚቆጠር መርዳትና መተባበር የሚችሉትን ፈፅሞ ሌላውን ጣጣ ለባለቤቱ ትቶ ዘወር ማለት ተገቢ በመሆኑ ልጅቷ ካለምንም ጥያቄ፡-
“ደህና ሁን” ብላው ስትሄድ ከወገቡ በፊት እጥፍ ብሎ
አጆቹን ዘርግቶ እጅዋን ያዛት: በግርምታ ዘወር ብላ አየችው አያት እሱም: ወዲያው ሃፍረት ተሰማው ወንጀለኝነት ስሜት አደረበት።የያዛት እጁ እጅዋን አለቀቀም። እሷም ለማስለቀቅ አልሞከረችም።
እጁ ግን ሲንቀጠቀጥ ይሰማታል። ስሜቱም ሲለዋወጥ ተመልክታዋለች። ስለዚህ ልታፈጥበት ልትገስፀው አልፈለገችም:
“አዝናለሁ" አላት ፈገግ
ለማለት ቢሞክርም ቅንድቡ
እየተንቀጠቀጠ እያሳጣው።
“ለምን?” አለችው በፅሞና።
“ትንሽ እንድትቆይ መጠየቅ በመፈልጌ..." አላት ቀስ ብሎ እየተጠጋ።
“ማዘን አያስፈልግህም! ቶሎ መሄድ ስላሰብኝ ግን አሁኑኑ መሄድ አለብኝ።" እጆቹን ኪሱ ከተተና አድራሻውን የያዘውን ካርድ
እየሰጣት “ብትችይ ደውይልኝ አላት በትህትና።
“አዝናለሁ” ትከሻዋን ሽቅብ ሰበቅ አድርጋ “ወደ አፍሪካ
መሄድ ስለምፈልግ ጊዜ የለኝም።''
“አፍሪካ...” ከነበረበት ቅዠት ሙሉ ለሙሉ ነቃ።
“አፍሪካ የት?" አላት ፊቱ ላይ ደስታ እየታዩ፡
“አያቴ አገር... ኢትዮጲያ” ስትለው አለከለከ: ድንጋጤ
አይሉት ደስታ ላብ እስኪያሰምጠው ድረስ ተሸበረ:
“ኢትዮጵያ!... ኢትዮጵያ... ኦ! አምላኬ እኔም ኢትዮጵያዊ ነኝ። የሃዘኔም ጦስ ናፍቆት ነው..." ሲል ልጅቷ አይኖችዋን አጥብ
ተመለከተችውና
“ኮንችት”
“ምን?”
“ፔሶ ቤኒ ኮንቺት እባላለሁ። ነገ በአስር ሰዓት እዚሁ እንገናኝ አለችውና ሄደች።
በግርምታ ከአይኑ እስክትጠፋ ተመለከታት።
“…አያቴ አገር ኢትዮጲያ... ያለችው እንደገና ጆሮው
ላይ አቃጨለበት ደስ አለው። ስለ ኢትዮጵያ አብሮት የሚያወራ
አግኝቷል፡ ከጉጉቱ የተነሳ ግን ነገ ራቀበት: ያን ሩቁን ነገ እንግዳውን ነገ. መጠበቅ ግን ግዴታው ነበር።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሶራ መኪናው ውስጥ ሆኖ በሃሣብ ፈረስ ከርቀት ደረቱን እንደ ጎረምሳ ገልብጦ ከሚመጣው የአትላንቲክ ውቅያኖስ ማዕበል ይገባና አብሮ ብቅ ጥልቅ እያለ እየሰጠመ እየተንሳፈፈ ወደ ዳር
ይመጣና ካለው የሲሚንቶ ግንብ ጋር እየተጋጨ እንደ ጥይት ጮሆ.አረፋ ሲደፍቅ... እራሱን እያዬ መሪው ላይ ተደፍቶ ሲጨነቅ ተመልሶ ደግሞ አይኖቹን ውቅያኖሱ ላይ ተክሎ በሃሣብ ለረጅም ጊዜ ሲንቦራጨቅ በምናቡ አለም መግቢያ ጠፍቶት ሲዛክር ቆዬ:
ቶዮታ ኮሮላ መኪና ቀስ እያለች አልፋ ክፍቱ የመኪና
ማቆሚያ ላይ ተስተካክላ ቆመችና ሞተሯ ጠፋ: ለተወሰነ ጊዜ ፀጥታው እንደገና ሰፈነ። ከዚያ የአስር ሰዓት ደወል ተሰማ።
👍23🔥2👎1🤔1
ታኮ ጫማ አጭር ስከርት ላዩ ላይ ቁልፎቹ ያልተቆለፉ
ካፖርት አንገቷ ላይ የአንገት መጎናፀፊያ የደረበች ሴት የቶዮታ መኪናዋን በር ከፍታ ወጣች: የመኪናዋን በር ገፋ አድርጋ ዘጋችና
ቁልፏን በጣቶችዋ እንዳንጠለጠለች ግራ ቀኝ ከይታ ፈጠን ብላ
ጠባቧን መንገድ ተሻግራ ወደ ሶራ አሮጌ ፊያት መኪና ተጠጋች።
ሶራ አይኖቹ እንደቦዙ በሃሣብ ጭልጥ ብሏል። የመኪናውን መስታዋት አንኳኩታ እጅዋን እያውለበለበች ፈገግ አለች። አላያትም! አልሰማትም:: ከፊት ለፊቱ ያለውን መስታዋት በእጆችዋ ስትጠበጥብ ድንገት ሲፀዳዳ የሽንት ቤት በር እንደከፈቱበት ሰው
ደንግጦ አያት: አዎ እሷ ናት: እንደአመታት ለረዘመ ስዓታት የጠበቃት እሷን ነው:: የመኪናውን በር
ከፍቶ ወጣ እጇን ዘረጋችለት ተጨባበጡ።
“እኔ ቤት ብንሄድ ምን ይመስልሃል?” ኮስተር ብላ በትህትና ጠየቀችው። እሽ በላት ቶሎ በል እሽ በል ስሜቱ አጣደፈው።
"ይቻላል” አለ ግራ ትከሻው ከፍ የግራ አይኑን ጨንቆር
አድርጎ።
“የምኖረው ሁዌልቫ ሳይሆን ሴቪልያ ነው፡ ስለዚህ
በየግላችን ዘጠና ኪሎሜትር መጓዝ አለብን: ምናልባት አርባ አምስት ደቂቃ ይፈጅብን ይሆናል። ተከታትለን ልንጓዝ እንችላለን
ብንጠፋፋ ግን ሴቪልያ ድልድዩን ካለፍህ በኋላ ኤክስፖ 92 ከተካሄደበት ከመድረስህ በፊት ወደ ግራ ትታጠፍና በጎዳና ቁጥር...
አፓርታማው ስር እጠብቅሃለሁ" ብላው ወደ መኪናዋ ሄደች::
“ሴፍቲ ቤልቱን አስሮ መኪናውን ካስነሳ በኋላ የሷን መኪና ተከትሎ ፍጥነቱን እየጨማመረ አሽከረከረ:
።።።።።።።።።።።።።።።።።
“ኦባቴ ኢትዮጵያዊ ነበር አልሽኝ?" አላት እሱ ሶፋው ላይ እሷ ደግሞ የሙዚቃ ዲስኬት እየመረጠች ከተሽከርካሪው ባለ
መስታዋት መደርደሪያ ፊት ለፊት እንደቆመች።
“አባቴ ሳይሆን አያቴ" አለችው ከወገቧ በላይ በቄንጠኛ አዟዟር ዞራ: ፈገግ ብሎ እራሱን በአዎንታ ወዘወዘና ዝም አለ። ገና
ጨዋታ ከመጀመሩ መሳሳቱ አሳዘነው: ቤቱ ውስጥ ሁለት ትላልቅ ፎቶ አለ: አንዱ የወንድ ሌላው የሴት
የወንዱ ፎቶ የአባቷ ወይም የአያቷ መሆን አለበት።
“ያ ፎቶ የአንች ነው ወይንስ የአባትሽ?
“የቱ" አለችው በተለመደው መልክ ዞራ። ጠቁሞ አሳያት
ከመመለሷ በፊት ግን፡
ምን ነበር የጠየቅከኝ?” አለችው::
ያ ፎቶ የአንች ነው ወይንስ
የአባትሽ?” አላት
እንደመቁነጥነጥ ብሎ: ኪሊሊ… ብላ ሳቀችና “ወንድና ሌት መለየት
አትችልም? ስትለው ደነገጠ።
ምነው! ምን ብዬ ጠየቅሁሽ? ፈገግ ለማለት እየሞከረ ያ ፎቶ የአንች ነው ወይንስ የአባትሽ ነውኮ ያልከኝ" አሁንም ሳቀች።
“የአባትሽ ነው ወይንስ የያትሽ ለማለት ፈልጎ ነው"
“ለነገሩ ገብቶኛል:: ጥያቄህ ግን በተለይ ስትደግመው
አሳቀኝ ይቅርታ እሽ የአያቴ ፎቶ ነው፡"
ምን ነካኝ፤ መረጋጋት አለብኝ፧ ካለበለዚያ ሴት ነሽ ወንድ' ብዬ መጠየቄ አይቀርም... ትዕግስት ያስፈልገኛል:: ደግሞ ዝም
ብልስ! ምን አስቀባጠረኝ። ፋይዳ ለሌለው ጥያቄ ግምት ውስጥ መግባት የለብኝም ... ሲል የመረጠችው ፊላሚንኮ ባህላዊ የስፔን ሙዚቃ መሰማት ጀመረ:: መሬቱን በቀኝ እግሯ መታ መታ
እጆችዋን ወደ ላይ አቁማ ጣቶችዋን እያዞረችና እያሽከረከረች...ስትደንስ ፈዞ ተመለከታት: ያምርባታል!
“ፊላሚንኮ ዳንስ ነው ትችላለህ? አላችው ቆም ብላ።
“አልችልም'' አላት
ሁስተኛው ፎቶ ላይ አይኖቹን አፈጠጠ: የዋና ፓንት የለበስች ከግራ ትከሻዋ ወዳ ዳሌዋ የወረደ ሪቫን በእጆችዋ የቁንጅና
በትረ ውበት የያዘች ቀኝ እግሯን ወደ ፊት ከወገቧ ትንሽ ወደኋላ ለጠጥ ብላ የቆመች ሴት ተመለከተ
ማናት?' ጠየቀ ራሱን።
ማንም ትሁን። ለምን ማወቅ ያስፈልገኛል: ኮንችት
የምታደንቃት የስፔን ውብ
በቃ! ሊረሳት ሞከረ:
ጠይቆ ማወቅ ምን ነውር አለው? ይልቅ ጠይቃት ፧
እየተሳሳቱ መጠየቅን መቀጠል እንዲያውም የጥንካሬ መለኪያ
ነው... ሁለተኛው ሃሣቡ አሸነፈ:
“ያች ደግሞ ማን የምትባል የስፔን ቆንጆ ናት? ጠየቃት
ጨከን ብሎ። አጠያየቁን ወደደው።
“ኮንችት ፔሶ ቤኒ ኮንችት” አለችው፡ ግራ ገባው: የእሷን
ስም ፔሶ ቤኒ ኮንችት እንዳለችው ያስታውሳል: ግን ደግሞ እሷ ትሆናለች የሚል ግምት አልነበረውም።
"በስም አንድ ናችሁ" በአጠያየቁ ኮራ:: ስሟን እንዳልረሳው
እግረ መንገዱን አስታወቃት።
“በስምም, በአካልም በመንፈስም አንድ ነን" አለችው ወደ ሌላ ክፍል ለመሄድ እያዘገመች። ጨነቀው እንደገና
“አንች ነሽ እንዴ?”
“አዎ እኔ ነኝ: በተለያዩ ጊዜያት የቁንጅና ውድድር
ተካፍያለሁ: ይሄ ያሸነፍኩበትና ሚስስ ካታሎንያ የተባልኩበት ነው።
ስራዬም እኮ ሞዴሊስትነት ነው'
አፉን በአድናቆት ከፈተ: መራጮችን አደነቃቸው: “ጎበዞች ቆንጆ ያውቃሉ" አለ ሳያስበው ከት ብላ ስትስቅበት ቅዠት ላይ
መሆኑን አወቀ: እየሳቀች ወደ ውስጥ ገባች
አራት በሮች ክፍሉ ውስጥ አሉ። አንዱ የገባበት ነው:
ሌሎችን አላወቀም፡
በአጋጣሚው እንደገና ተገረመ፤ በበታችነት ስሜት ስሜቱ እጁን ሲያጥፍ ተሰማው፡ ተስፋ የመቁረጥ ስሜትም አደረበት በሃሣቡ ራሱን ብቸኝነትን ፈንቅዬ ወጣሁ ወዳለበት ጉድጓድ ተመልሶ ሲገባ አየው።
ኮንችት በሩን ከፍታ ገባች።
“አያቴ ኢትዮጵያዊ መሆኑን የደረሰበት ከብዙ ልፋትና
ድካም በኋላ ቢሆንም በአፍለኛ የወጣትነት ዘመኑ አፍሪካዊ መሆኑን
በሚገባ ያውቅ ነበር: ኋላ ግን በግል ጥረቱ የአፍሪካን ምድር ከቱኒሲያ እስከ ደቡብ አፍሪካ ከዚያም ከፊል ጥርጣሬው አይሉ
ወደነበረበት ወደ ምዕራብ አፍሪካ ቢጓዝም እንዳሰበው በልጅነቱ
ጥሎት የወጣውን የአባቱን አገር ማወቅ አልቻለም ነበር" አለችና፡
“እንዴ ይቅርታ ወደ ጓዳ ገባ ልበልና የሚበላላውን
ላዘጋጅ:: ከዚህ በፊት ግን ቺቫስ ሪጋል ሬሚ ማርቲን፤ ጆኒ ወከር! ብላክ ሌብል ሄግ ውስኪ የሚጠጣ አለልህ፤ ቤንሰን ማርልቦሮ
ዊንስተን ሲጋራዎች እኒሁልህ: ፍሪጅ ውስጥ ለስላሳ ቢራ በረዶም... አለ ሙዚቃው የእኔ ምርጫ በመሆኑ ይቅርታ እሱንም
ካሉኝ ዲስኬቶች መርጠህ ያሻህን ማዳመጥ ትችላለህ ቤተኛ ሁን እሽ ብላ ፈገግታዋን አፍስሳበት ገባች:
ሶራ ፈገግ ብሎ ለምስጋናው ምላሽ አቅርቦ ወደ ውስጥ
ስትጀባ የሰውነት ቅርጿን ትኩር ብሎ ተመለከተ: የለበሰችው አጭር
ቀሚስ ወልቆ ስስ ጋዋን ስትለብስ የሰውነቷን ቅርፅ እንደ አጉሊ መነፅር አጉልቶ የሚያሳይ እስኪመስለው ጠባብ ትከሻዋ ስርጓዳ
ወገቧ የሚያማምሩት እግሮችዋ... ቁልጭ ብለው ታዩት።
ነጩ ፓንቷ የሴትነት ብልቷ… እራቁቷን እንኳ ብትሆን
ያን ሁሉ የሚያይ አልመሰለውም:
ከገባች በኋላም ቅርጿን ለማስታወስ ፈለገ።
'ለምን? ጊዜ አለኝ። የዚችን ቆንጆ ምስል ህሊናዩ
በሚፈጥረው ቅርፅ እያሰብሁ ማበላሽት የለብኝም አለና የቺቫዝ
ሪጋሉን ጠርሙዝ አንስቶ በብርጭቆ ጨመረና ከፍሪጁ በረዶ አውጥቶ ሁለት እንክብል ጨምሮ ነቅነቅ በማድረግና ወደ ከንፈሩ አስጠጋው። ከዚያም ወደ መስቱ ጠጋ ብሉ በነጩ መጋረጃ ቁልቁል ተመለከተ። መንገዱ ላይ ሰዎች ተሽከርካሪዎች... ይርመሰመሳሉ። ህፃናት ከመንገዱ ማዶ ዥዋ ዥዌ ኳስ በሮለር ብሌድ መንሸራተቻ ይጫወታሉ።
ሶራ ውስኪ የያዘ ብርጭቆውን አስቀምጦ የሲጋራ ፓኮውን ሲያነሳ “ጠሽ ጠሽ" የሚል ድምፅ ቀጥሎ የምግብ ሽታ አወደው። ያኔ ረሃብ ተሰማው፡ በሆዱ ፍላጎት የተስማማ አይመስልም::
ህሊናው በራበው ግን ተስማምቷል። ያን ሊገልፁት የሚከብድ ገላ እንደገና ማየት…..
💫ይቀጥላል💫
ካፖርት አንገቷ ላይ የአንገት መጎናፀፊያ የደረበች ሴት የቶዮታ መኪናዋን በር ከፍታ ወጣች: የመኪናዋን በር ገፋ አድርጋ ዘጋችና
ቁልፏን በጣቶችዋ እንዳንጠለጠለች ግራ ቀኝ ከይታ ፈጠን ብላ
ጠባቧን መንገድ ተሻግራ ወደ ሶራ አሮጌ ፊያት መኪና ተጠጋች።
ሶራ አይኖቹ እንደቦዙ በሃሣብ ጭልጥ ብሏል። የመኪናውን መስታዋት አንኳኩታ እጅዋን እያውለበለበች ፈገግ አለች። አላያትም! አልሰማትም:: ከፊት ለፊቱ ያለውን መስታዋት በእጆችዋ ስትጠበጥብ ድንገት ሲፀዳዳ የሽንት ቤት በር እንደከፈቱበት ሰው
ደንግጦ አያት: አዎ እሷ ናት: እንደአመታት ለረዘመ ስዓታት የጠበቃት እሷን ነው:: የመኪናውን በር
ከፍቶ ወጣ እጇን ዘረጋችለት ተጨባበጡ።
“እኔ ቤት ብንሄድ ምን ይመስልሃል?” ኮስተር ብላ በትህትና ጠየቀችው። እሽ በላት ቶሎ በል እሽ በል ስሜቱ አጣደፈው።
"ይቻላል” አለ ግራ ትከሻው ከፍ የግራ አይኑን ጨንቆር
አድርጎ።
“የምኖረው ሁዌልቫ ሳይሆን ሴቪልያ ነው፡ ስለዚህ
በየግላችን ዘጠና ኪሎሜትር መጓዝ አለብን: ምናልባት አርባ አምስት ደቂቃ ይፈጅብን ይሆናል። ተከታትለን ልንጓዝ እንችላለን
ብንጠፋፋ ግን ሴቪልያ ድልድዩን ካለፍህ በኋላ ኤክስፖ 92 ከተካሄደበት ከመድረስህ በፊት ወደ ግራ ትታጠፍና በጎዳና ቁጥር...
አፓርታማው ስር እጠብቅሃለሁ" ብላው ወደ መኪናዋ ሄደች::
“ሴፍቲ ቤልቱን አስሮ መኪናውን ካስነሳ በኋላ የሷን መኪና ተከትሎ ፍጥነቱን እየጨማመረ አሽከረከረ:
።።።።።።።።።።።።።።።።።
“ኦባቴ ኢትዮጵያዊ ነበር አልሽኝ?" አላት እሱ ሶፋው ላይ እሷ ደግሞ የሙዚቃ ዲስኬት እየመረጠች ከተሽከርካሪው ባለ
መስታዋት መደርደሪያ ፊት ለፊት እንደቆመች።
“አባቴ ሳይሆን አያቴ" አለችው ከወገቧ በላይ በቄንጠኛ አዟዟር ዞራ: ፈገግ ብሎ እራሱን በአዎንታ ወዘወዘና ዝም አለ። ገና
ጨዋታ ከመጀመሩ መሳሳቱ አሳዘነው: ቤቱ ውስጥ ሁለት ትላልቅ ፎቶ አለ: አንዱ የወንድ ሌላው የሴት
የወንዱ ፎቶ የአባቷ ወይም የአያቷ መሆን አለበት።
“ያ ፎቶ የአንች ነው ወይንስ የአባትሽ?
“የቱ" አለችው በተለመደው መልክ ዞራ። ጠቁሞ አሳያት
ከመመለሷ በፊት ግን፡
ምን ነበር የጠየቅከኝ?” አለችው::
ያ ፎቶ የአንች ነው ወይንስ
የአባትሽ?” አላት
እንደመቁነጥነጥ ብሎ: ኪሊሊ… ብላ ሳቀችና “ወንድና ሌት መለየት
አትችልም? ስትለው ደነገጠ።
ምነው! ምን ብዬ ጠየቅሁሽ? ፈገግ ለማለት እየሞከረ ያ ፎቶ የአንች ነው ወይንስ የአባትሽ ነውኮ ያልከኝ" አሁንም ሳቀች።
“የአባትሽ ነው ወይንስ የያትሽ ለማለት ፈልጎ ነው"
“ለነገሩ ገብቶኛል:: ጥያቄህ ግን በተለይ ስትደግመው
አሳቀኝ ይቅርታ እሽ የአያቴ ፎቶ ነው፡"
ምን ነካኝ፤ መረጋጋት አለብኝ፧ ካለበለዚያ ሴት ነሽ ወንድ' ብዬ መጠየቄ አይቀርም... ትዕግስት ያስፈልገኛል:: ደግሞ ዝም
ብልስ! ምን አስቀባጠረኝ። ፋይዳ ለሌለው ጥያቄ ግምት ውስጥ መግባት የለብኝም ... ሲል የመረጠችው ፊላሚንኮ ባህላዊ የስፔን ሙዚቃ መሰማት ጀመረ:: መሬቱን በቀኝ እግሯ መታ መታ
እጆችዋን ወደ ላይ አቁማ ጣቶችዋን እያዞረችና እያሽከረከረች...ስትደንስ ፈዞ ተመለከታት: ያምርባታል!
“ፊላሚንኮ ዳንስ ነው ትችላለህ? አላችው ቆም ብላ።
“አልችልም'' አላት
ሁስተኛው ፎቶ ላይ አይኖቹን አፈጠጠ: የዋና ፓንት የለበስች ከግራ ትከሻዋ ወዳ ዳሌዋ የወረደ ሪቫን በእጆችዋ የቁንጅና
በትረ ውበት የያዘች ቀኝ እግሯን ወደ ፊት ከወገቧ ትንሽ ወደኋላ ለጠጥ ብላ የቆመች ሴት ተመለከተ
ማናት?' ጠየቀ ራሱን።
ማንም ትሁን። ለምን ማወቅ ያስፈልገኛል: ኮንችት
የምታደንቃት የስፔን ውብ
በቃ! ሊረሳት ሞከረ:
ጠይቆ ማወቅ ምን ነውር አለው? ይልቅ ጠይቃት ፧
እየተሳሳቱ መጠየቅን መቀጠል እንዲያውም የጥንካሬ መለኪያ
ነው... ሁለተኛው ሃሣቡ አሸነፈ:
“ያች ደግሞ ማን የምትባል የስፔን ቆንጆ ናት? ጠየቃት
ጨከን ብሎ። አጠያየቁን ወደደው።
“ኮንችት ፔሶ ቤኒ ኮንችት” አለችው፡ ግራ ገባው: የእሷን
ስም ፔሶ ቤኒ ኮንችት እንዳለችው ያስታውሳል: ግን ደግሞ እሷ ትሆናለች የሚል ግምት አልነበረውም።
"በስም አንድ ናችሁ" በአጠያየቁ ኮራ:: ስሟን እንዳልረሳው
እግረ መንገዱን አስታወቃት።
“በስምም, በአካልም በመንፈስም አንድ ነን" አለችው ወደ ሌላ ክፍል ለመሄድ እያዘገመች። ጨነቀው እንደገና
“አንች ነሽ እንዴ?”
“አዎ እኔ ነኝ: በተለያዩ ጊዜያት የቁንጅና ውድድር
ተካፍያለሁ: ይሄ ያሸነፍኩበትና ሚስስ ካታሎንያ የተባልኩበት ነው።
ስራዬም እኮ ሞዴሊስትነት ነው'
አፉን በአድናቆት ከፈተ: መራጮችን አደነቃቸው: “ጎበዞች ቆንጆ ያውቃሉ" አለ ሳያስበው ከት ብላ ስትስቅበት ቅዠት ላይ
መሆኑን አወቀ: እየሳቀች ወደ ውስጥ ገባች
አራት በሮች ክፍሉ ውስጥ አሉ። አንዱ የገባበት ነው:
ሌሎችን አላወቀም፡
በአጋጣሚው እንደገና ተገረመ፤ በበታችነት ስሜት ስሜቱ እጁን ሲያጥፍ ተሰማው፡ ተስፋ የመቁረጥ ስሜትም አደረበት በሃሣቡ ራሱን ብቸኝነትን ፈንቅዬ ወጣሁ ወዳለበት ጉድጓድ ተመልሶ ሲገባ አየው።
ኮንችት በሩን ከፍታ ገባች።
“አያቴ ኢትዮጵያዊ መሆኑን የደረሰበት ከብዙ ልፋትና
ድካም በኋላ ቢሆንም በአፍለኛ የወጣትነት ዘመኑ አፍሪካዊ መሆኑን
በሚገባ ያውቅ ነበር: ኋላ ግን በግል ጥረቱ የአፍሪካን ምድር ከቱኒሲያ እስከ ደቡብ አፍሪካ ከዚያም ከፊል ጥርጣሬው አይሉ
ወደነበረበት ወደ ምዕራብ አፍሪካ ቢጓዝም እንዳሰበው በልጅነቱ
ጥሎት የወጣውን የአባቱን አገር ማወቅ አልቻለም ነበር" አለችና፡
“እንዴ ይቅርታ ወደ ጓዳ ገባ ልበልና የሚበላላውን
ላዘጋጅ:: ከዚህ በፊት ግን ቺቫስ ሪጋል ሬሚ ማርቲን፤ ጆኒ ወከር! ብላክ ሌብል ሄግ ውስኪ የሚጠጣ አለልህ፤ ቤንሰን ማርልቦሮ
ዊንስተን ሲጋራዎች እኒሁልህ: ፍሪጅ ውስጥ ለስላሳ ቢራ በረዶም... አለ ሙዚቃው የእኔ ምርጫ በመሆኑ ይቅርታ እሱንም
ካሉኝ ዲስኬቶች መርጠህ ያሻህን ማዳመጥ ትችላለህ ቤተኛ ሁን እሽ ብላ ፈገግታዋን አፍስሳበት ገባች:
ሶራ ፈገግ ብሎ ለምስጋናው ምላሽ አቅርቦ ወደ ውስጥ
ስትጀባ የሰውነት ቅርጿን ትኩር ብሎ ተመለከተ: የለበሰችው አጭር
ቀሚስ ወልቆ ስስ ጋዋን ስትለብስ የሰውነቷን ቅርፅ እንደ አጉሊ መነፅር አጉልቶ የሚያሳይ እስኪመስለው ጠባብ ትከሻዋ ስርጓዳ
ወገቧ የሚያማምሩት እግሮችዋ... ቁልጭ ብለው ታዩት።
ነጩ ፓንቷ የሴትነት ብልቷ… እራቁቷን እንኳ ብትሆን
ያን ሁሉ የሚያይ አልመሰለውም:
ከገባች በኋላም ቅርጿን ለማስታወስ ፈለገ።
'ለምን? ጊዜ አለኝ። የዚችን ቆንጆ ምስል ህሊናዩ
በሚፈጥረው ቅርፅ እያሰብሁ ማበላሽት የለብኝም አለና የቺቫዝ
ሪጋሉን ጠርሙዝ አንስቶ በብርጭቆ ጨመረና ከፍሪጁ በረዶ አውጥቶ ሁለት እንክብል ጨምሮ ነቅነቅ በማድረግና ወደ ከንፈሩ አስጠጋው። ከዚያም ወደ መስቱ ጠጋ ብሉ በነጩ መጋረጃ ቁልቁል ተመለከተ። መንገዱ ላይ ሰዎች ተሽከርካሪዎች... ይርመሰመሳሉ። ህፃናት ከመንገዱ ማዶ ዥዋ ዥዌ ኳስ በሮለር ብሌድ መንሸራተቻ ይጫወታሉ።
ሶራ ውስኪ የያዘ ብርጭቆውን አስቀምጦ የሲጋራ ፓኮውን ሲያነሳ “ጠሽ ጠሽ" የሚል ድምፅ ቀጥሎ የምግብ ሽታ አወደው። ያኔ ረሃብ ተሰማው፡ በሆዱ ፍላጎት የተስማማ አይመስልም::
ህሊናው በራበው ግን ተስማምቷል። ያን ሊገልፁት የሚከብድ ገላ እንደገና ማየት…..
💫ይቀጥላል💫
👍37❤1
‹‹የተሰባበሩ ነፍሶች››
ምዕራፍ- 15
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
////
እሺ ጀግናው.አመጣህልኝ››
አይ ጌታዬ ችግረ ተፈጥሮለል››የጋለ ሰውነቱ ሲቀዘቅዝ ተሰማው
ይሄውልህ አንድ ግዜ በእንቤታ በተንፈራገጥሽ ቁጥር በእጄ ከሉት ዘመዶቾ አንዱን እንደምገድ ነገራት ሁለተኘውን ስትደግም ደግሞ ሌለኛውን..››
እንደዛ ከሆነ ጥሩ
‹‹እሺ ጀግናው…አመጣህልኝ?››
‹‹አይ ጌታዬ ችግር ተፈጥሮል››የጋለ ሰውነቱ ሲቀዘቅዝ ተሰማው
‹ይሄውልህ አንድ ግዜ በእንቢታ በተንፈራገጥሽ ቁጥር በእጄ ከሉት ዘመዶቾ አንዱን እንደምገድ ንገራት ሁለተኛውን ስትደግም ደግሞ ሌለኛውን..እንደውም ስልኩን ጆሮዋ ላይ ለጥፍልኝ››
‹‹ጌታዬ እንደዛ አይደለም፡፡ ከእኔ በፊት አራት ሰዎች ቀድመው ደርሰው አፍነዋታል፡፡አብሮትም አንድ ሰው ነበር ፤ሁለቱንም ነው ያፈኗቸው፡፡››
ምን እያልከኝ ነው… ማን ሊሆን ይችላል?›
‹‹አላወቅኩም . .ጌታዬ….››
‹‹የመንግስት ሰው ናቸው .ማለቴ ፖሊሶች ናቸው?›
‹አይ ፖሊሶች እንኳን አይደሉም..ማለቴ የፖሊስ ለብስ አለበሱም››
‹‹በቃ ደህንነቶች ይሆናሉ›እንግዲያው ቀስ ብለህ ከኃላህ ተከተላቸውና የት እንደሚወስዷት አጣራ…ጓደኖችህን አሁን ልካቸዋለው፡፡››
ስልኩን ዘጋና እጁን ወደፊት በቡጢ ሰነዘረ ፊት ለፊቱ ያለው ደግሞ የመስተወት መስኮት ነበር.. ተፈረካከሰ ፡፡የእጁን ጣት ሸረከተው..ደሙ መንጠባጠብ ጀመረ…ግድም አልሰጠውም፡፡
‹ስልኩን አነሰሳና አቶ ሙላ ጋር ደወለ.›
‹ስማ አንተ…እነዛ ባለስልጣኖች ምን እየሰሩ ነው?››
‹‹ምን ሰሩ?››
‹‹ይሄው የሴትዬዋን ቤተሰቦች አግቼ በእቅዴ መሰረት መልዕቱ እንዲደርሳት አድርጌ ነበር…እሷም ሁለት ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ነበር እየሮጠች እቤቴ የመጣቸው
‹‹እቤቴ ደስ ሲል እና ነገሩ አለቀ በለኛ! ከጉድ ወጠን ማለት ነው…እና ገደልካት?›አለ አቶ ሙሉ በሚፈነጥዝ ድምፀ
‹‹እስኪ መቀባጠርህን አቁመህ አድመጠኝ››
‹እያዳመጥኩህ ነው .ምን ተፈጠረ?››
‹‹ከእኔ ቤት ወደአለሁበት ቦታ የሚያመጣት ሰው ልኬ ነበር.. ልጁ እዛ ሲደርስ ግን ሌላ ሀይል ቀድሞ ደርሶ አፍኖ ወደ ሆነ ቦታ እየወሰዶት ነው ››.
‹‹ማን ነው እንደዛ የሚያደርገው…?››
ማን ይሆናል .እንደዛ የማድረግ ኃይል ያላቸው እነዛ ባለስልጣናት ብቻ ናቸው…እና አሁን የእኔ ሰው እየተከተላቸው ነው…. አሁን ደውልና መኪናቸወን አቁመው ልጅቷን አስረክበውን ወደሚሔዱበት እንዲሄዱ ንገራቸው፡ ካልሆነ ከ30 ደቂቃ ቡኃላ ጉዳቸውን ለመለው አለም ነው የምነዛው››
‹‹አረ ፕሮፌሰር ተረጋጋ..እነሱ ምን ለማትረፍ እንዲህ ያደርጋሉ.በችኮላ የማይሆን ነገር አድርገህ ሁላችንንም ገደል እንዳትከተን››ሲል ፋራቸውን ገለፀለት፡
ምን ሊያገኙ አልክ…አሁን እኮ እሷ ማለት ለሁላችንም ትልቅ መጫወቻ ካርድ ነች….እሷን ያገኘ እራሱን ማዳን ብቻ ሳይሆን ጠላቴ ነው አያስፈልገኝም ያለውን ሰውም ያጠፋበታል.››
‹‹እና አንተ እጅህ ብትገባ እንደዛ የማድረግ እቅድ ነበረህ ››
‹‹አዎ ነበረኝ ግን.አንተ ከጠላቶቼ መካከል አይደለህም…ምነው ነህ እነዴ?›
ተርበተበተ‹‹ፕሮፌሰር የምን ጠላት አመጣህብኝ..በቃ አሁን ደውልላቸዋለው››
ስልኩ ተዘጋ…የእጁ ደም አሁንም እየተነጠባተበ ነወ..ከቆመበት ሳይንቀሳቀስ የመጋረጃን ጨርቅ ከጨጫፍ ይዞ ሸረከተና ጠቀለለው፡ከዛ ስልኩን አነሳና ደወለ…ከብዙ ጥሪ ብኃላ ተነሳለት
አንተ ሰው እኔ እኮ ሽማጊሌ ነኝ በውድቅት ሊት አትደወውልልኝ ብልህ አልሰመ አልከኝ››በወቀሳ ተቀበሉት
ሼኪ ይቀልዳሉ እንዴ.መቼሰ በጣም አስቸጋሪ ነገር ባይፈጠር በዚህ ሰዓት አልደውልም›
ነገርኩህ እኮ ጥዋት ይደርሳል..ደግሞ ምንም ቢከሰት ትወጠጣዋለህ.›
‹ያሾፋሉ አይደል…አሺ እንዳለሉት እወጣዋለው.. አሁን በቀደም እዘጋጁ ያልኮትን ዶላር ነገ ያቀብሉኛል..ከሳይውል ሳያድር ከሀገር መውጣጣት አለብኝ፡፡
እ..እስኪ ፈልጋለው..አለ ያልኩህን ሌጄ ለእኔ ሳሳነግር ለጉዳይ ተጠቅሞበታል.እስኪ ሰሞኑን ከዚህም ከዛም እንፈልጋለን›
በሼኪወው ንግግር እምሮውን ሊስት ትንሽ ነው የቀረው‹ሴኪ ያለንበት ስቺዌሽን ግልፅ ሆነሎት አይመስለኝም..ከገባን ሁለቻንም ንነ ን መቀመቅ ውጥ የምንገባው…..ለሁላችንም የምለፋው እኮ እርሶ ትልቅ ሰው ኖት በዚሀህ እድሜየት መንገላታት የለቦትም ብዬ ነው.እረሶ ግን
‹ስማ ፕሮፌሰር በል አሁ ተኛ ቸው›ስልኩን ጆሮው ላይ ዘጉበት፡፡
ማመን አልቻለም…እኚ ሰውዬ ማን ነው አይዞችሁ ያላቸው…እንዴት ነው እንዲህ ሊንቀባሩብኝ የቻሉት፡፡ወይ እምሮቸውን ስተዋል…ወይ ተስፋ ቆርጠዋል ወይ ደግሞ የሆነ እኔ ያልደረስኩበት ሚስጠጥር በእጃቸው ገብቷል..ደከመውና እዛው በቆመበት ሸርት ብሎ ወል ላይ ጠቀመጠ
ታዲያ ጉዳዩን እራስህ በጥነንቃቄ ምራው..ምንም ችግር እንዲፈተረር አልፈልግም.እናም ደግመ ማንኛቸውም እንዳይጎዱ›
የፕሮፌሰሩ መልዕክተኛ ከፕሮፌሰሩu ጋር አያወራ የነበረው ከመኪናው ወጥ ገቢናውን ተደግፎ ነበር..አውርቶ ከጨረሰ ብሃላ እንደታዘው መኪናዋን ለመከተል ወደመኪናው ሊገባ ሲል ከኃላው ማጀራቱ ላይ ቀዝቀቃዛ ብረት አረፈ..ሊዞር ሲል
‹‹ቀጥ ብለህ ባለህበት ቁም››የሚል ድምፅ አስጠነቀቀው…እንደተባለው አደረገ፡፡.ትዘዛዙን አክብሮ ገባና የሹፌሩን ቦታ ያዘ..ሌለኛው ዞሮ ገባና ከጎኑ ተቀመጠ…ሽጉጥ የደቀነው በጥንቃቄ የሃላውን በራፍ ከፍቶ ገባ…ሽጉጡን በጭንቅላቱ አስተካክሎ አንደቀነበት ነው፡ገቢና ከጎኑ ያለው ዘና ብሎ ስልክ አውጥቶ ደወለ..
‹ሄሎ ስንደርስ ይዛዋት ሄደዋል .ግን አንድ የእነሱን ሰው ከነመኪናው ይዘነዋ… ምን እናድርገው?፡፡›ታጋቹ እንዲሰማው ሞባይሉን ላውድ ላይ አደረገ…
‹‹ከፈለጋችሁ ሰባብሩት..ካልሆነም ቆራርጡትና ቀጥታ ወደ ወሰዷት ቦታ እንዲመራችሁ አድርጉ፡፡እነአቤሎም ወደ እናተ እንዲመጡ አ,እና እንዲያግዛችሁ አደርጋለው … እኔም መጣሁ››ስልኩ ተዘጋ፡
‹ሀለቃችን ያለውን ሰምተሀል አይደል?፡፡›
‹አዎ ሰምቼያለው…..››
‹‹ስለዚህ እነደማይ አንተም እንደ እኛ ባለሞያ ነህ… ስለዚህ ከአንተ ጠብ የለንም…ጓደኞችህ ወደየት ነው የወሰዶቸው?››
‹‹አልገባችሁም..ሰዎቹ ጎደኞቼ አይደሉም…በእርግጥ እኔ ፕሮፌሰሩ ሂድና አምጣት ብሎኝ ነበር የመጣሁት…እራሷ ደውላ ውሰደኝ ስላለችው ኃይል ና ግርግር ስለማያስፈልግ ብቻዬን ነበር የመጣሁት፡፡ ስደርስ ግን አራት የታጠቁና የተደራጁ አፋኞች መኪናዋ ውስጥ ሲከቷት ደረስኩ፡፡ለሀለቃዬ ደውዬ ስነግረው ተከተላቸውና የገቡበትን እይ ብሎኝ ነበር..›
‹‹እናስ?›
‹‹እናማ እናንተ አሰናከላችሁኝ ..››
‹እስኪ ፍጠን ሞተሩን አስነሳው..በየት ነው የሄዱት፣በፊት ለፊት ሄደው ማደያው ጋ ሲደርሱ ወደግራ ነው የታጠፉት…››
‹ንዳው.ንዳው›ጮኸበት፡፡
መዳው.. ወደግራ ታጠፉ ፡፡አንድ ኪሎ ሜትር ያህል ዙሪያ ገባቸውን እቃኙ ቢበሩም የተባለችውን መኪና ሊያገኞት አልቻሉም…
መልሶ ደወለለት…ለአብዬት…ያለውን ነገረው..፡፡
‹‹እወነቱን ከሆነ ፕሮፌሰሩ ጋር ይውሰዳችሁ….አሳልፎ ይስጣችሁ እሱን ይዛችሁልኝ ኑ..››
‹‹እሺ››
‹‹ነግሬሀለው ስህተት አልፈልግም..ወይ ዶክተሯንና ካሳን ወይም ደግሞ ፕሮፌሰሩን አሁኑኑ ፈልጋለው..››ስልኩ ተዘጋ
‹‹ያው የስራውን አካሄድ ምታውቅው ነው…አንተ ላይ ብጢ መሰንዘር ወይ ደግሞ ተኩሶ ተፋህን መበርቀስ አልፈልግም…..ካልሆነ ግን
‹‹ጓደኛዬ ላይም ሆነ እኔ ላይ ምንም አደጋ እንዲደርስ አልፈልግም››መለሰ
‹‹ነገርኩህ እኮ..እንደው ቀልል እንዲል ካደረጋችሁ ለሀለቃችን በማስረዳ ከዚህ ያጣችሁትን ስራ እኛ ጋር እንድታገኙ ማድረግ እንችላለን፡፡
ምዕራፍ- 15
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
////
እሺ ጀግናው.አመጣህልኝ››
አይ ጌታዬ ችግረ ተፈጥሮለል››የጋለ ሰውነቱ ሲቀዘቅዝ ተሰማው
ይሄውልህ አንድ ግዜ በእንቤታ በተንፈራገጥሽ ቁጥር በእጄ ከሉት ዘመዶቾ አንዱን እንደምገድ ነገራት ሁለተኘውን ስትደግም ደግሞ ሌለኛውን..››
እንደዛ ከሆነ ጥሩ
‹‹እሺ ጀግናው…አመጣህልኝ?››
‹‹አይ ጌታዬ ችግር ተፈጥሮል››የጋለ ሰውነቱ ሲቀዘቅዝ ተሰማው
‹ይሄውልህ አንድ ግዜ በእንቢታ በተንፈራገጥሽ ቁጥር በእጄ ከሉት ዘመዶቾ አንዱን እንደምገድ ንገራት ሁለተኛውን ስትደግም ደግሞ ሌለኛውን..እንደውም ስልኩን ጆሮዋ ላይ ለጥፍልኝ››
‹‹ጌታዬ እንደዛ አይደለም፡፡ ከእኔ በፊት አራት ሰዎች ቀድመው ደርሰው አፍነዋታል፡፡አብሮትም አንድ ሰው ነበር ፤ሁለቱንም ነው ያፈኗቸው፡፡››
ምን እያልከኝ ነው… ማን ሊሆን ይችላል?›
‹‹አላወቅኩም . .ጌታዬ….››
‹‹የመንግስት ሰው ናቸው .ማለቴ ፖሊሶች ናቸው?›
‹አይ ፖሊሶች እንኳን አይደሉም..ማለቴ የፖሊስ ለብስ አለበሱም››
‹‹በቃ ደህንነቶች ይሆናሉ›እንግዲያው ቀስ ብለህ ከኃላህ ተከተላቸውና የት እንደሚወስዷት አጣራ…ጓደኖችህን አሁን ልካቸዋለው፡፡››
ስልኩን ዘጋና እጁን ወደፊት በቡጢ ሰነዘረ ፊት ለፊቱ ያለው ደግሞ የመስተወት መስኮት ነበር.. ተፈረካከሰ ፡፡የእጁን ጣት ሸረከተው..ደሙ መንጠባጠብ ጀመረ…ግድም አልሰጠውም፡፡
‹ስልኩን አነሰሳና አቶ ሙላ ጋር ደወለ.›
‹ስማ አንተ…እነዛ ባለስልጣኖች ምን እየሰሩ ነው?››
‹‹ምን ሰሩ?››
‹‹ይሄው የሴትዬዋን ቤተሰቦች አግቼ በእቅዴ መሰረት መልዕቱ እንዲደርሳት አድርጌ ነበር…እሷም ሁለት ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ነበር እየሮጠች እቤቴ የመጣቸው
‹‹እቤቴ ደስ ሲል እና ነገሩ አለቀ በለኛ! ከጉድ ወጠን ማለት ነው…እና ገደልካት?›አለ አቶ ሙሉ በሚፈነጥዝ ድምፀ
‹‹እስኪ መቀባጠርህን አቁመህ አድመጠኝ››
‹እያዳመጥኩህ ነው .ምን ተፈጠረ?››
‹‹ከእኔ ቤት ወደአለሁበት ቦታ የሚያመጣት ሰው ልኬ ነበር.. ልጁ እዛ ሲደርስ ግን ሌላ ሀይል ቀድሞ ደርሶ አፍኖ ወደ ሆነ ቦታ እየወሰዶት ነው ››.
‹‹ማን ነው እንደዛ የሚያደርገው…?››
ማን ይሆናል .እንደዛ የማድረግ ኃይል ያላቸው እነዛ ባለስልጣናት ብቻ ናቸው…እና አሁን የእኔ ሰው እየተከተላቸው ነው…. አሁን ደውልና መኪናቸወን አቁመው ልጅቷን አስረክበውን ወደሚሔዱበት እንዲሄዱ ንገራቸው፡ ካልሆነ ከ30 ደቂቃ ቡኃላ ጉዳቸውን ለመለው አለም ነው የምነዛው››
‹‹አረ ፕሮፌሰር ተረጋጋ..እነሱ ምን ለማትረፍ እንዲህ ያደርጋሉ.በችኮላ የማይሆን ነገር አድርገህ ሁላችንንም ገደል እንዳትከተን››ሲል ፋራቸውን ገለፀለት፡
ምን ሊያገኙ አልክ…አሁን እኮ እሷ ማለት ለሁላችንም ትልቅ መጫወቻ ካርድ ነች….እሷን ያገኘ እራሱን ማዳን ብቻ ሳይሆን ጠላቴ ነው አያስፈልገኝም ያለውን ሰውም ያጠፋበታል.››
‹‹እና አንተ እጅህ ብትገባ እንደዛ የማድረግ እቅድ ነበረህ ››
‹‹አዎ ነበረኝ ግን.አንተ ከጠላቶቼ መካከል አይደለህም…ምነው ነህ እነዴ?›
ተርበተበተ‹‹ፕሮፌሰር የምን ጠላት አመጣህብኝ..በቃ አሁን ደውልላቸዋለው››
ስልኩ ተዘጋ…የእጁ ደም አሁንም እየተነጠባተበ ነወ..ከቆመበት ሳይንቀሳቀስ የመጋረጃን ጨርቅ ከጨጫፍ ይዞ ሸረከተና ጠቀለለው፡ከዛ ስልኩን አነሳና ደወለ…ከብዙ ጥሪ ብኃላ ተነሳለት
አንተ ሰው እኔ እኮ ሽማጊሌ ነኝ በውድቅት ሊት አትደወውልልኝ ብልህ አልሰመ አልከኝ››በወቀሳ ተቀበሉት
ሼኪ ይቀልዳሉ እንዴ.መቼሰ በጣም አስቸጋሪ ነገር ባይፈጠር በዚህ ሰዓት አልደውልም›
ነገርኩህ እኮ ጥዋት ይደርሳል..ደግሞ ምንም ቢከሰት ትወጠጣዋለህ.›
‹ያሾፋሉ አይደል…አሺ እንዳለሉት እወጣዋለው.. አሁን በቀደም እዘጋጁ ያልኮትን ዶላር ነገ ያቀብሉኛል..ከሳይውል ሳያድር ከሀገር መውጣጣት አለብኝ፡፡
እ..እስኪ ፈልጋለው..አለ ያልኩህን ሌጄ ለእኔ ሳሳነግር ለጉዳይ ተጠቅሞበታል.እስኪ ሰሞኑን ከዚህም ከዛም እንፈልጋለን›
በሼኪወው ንግግር እምሮውን ሊስት ትንሽ ነው የቀረው‹ሴኪ ያለንበት ስቺዌሽን ግልፅ ሆነሎት አይመስለኝም..ከገባን ሁለቻንም ንነ ን መቀመቅ ውጥ የምንገባው…..ለሁላችንም የምለፋው እኮ እርሶ ትልቅ ሰው ኖት በዚሀህ እድሜየት መንገላታት የለቦትም ብዬ ነው.እረሶ ግን
‹ስማ ፕሮፌሰር በል አሁ ተኛ ቸው›ስልኩን ጆሮው ላይ ዘጉበት፡፡
ማመን አልቻለም…እኚ ሰውዬ ማን ነው አይዞችሁ ያላቸው…እንዴት ነው እንዲህ ሊንቀባሩብኝ የቻሉት፡፡ወይ እምሮቸውን ስተዋል…ወይ ተስፋ ቆርጠዋል ወይ ደግሞ የሆነ እኔ ያልደረስኩበት ሚስጠጥር በእጃቸው ገብቷል..ደከመውና እዛው በቆመበት ሸርት ብሎ ወል ላይ ጠቀመጠ
ታዲያ ጉዳዩን እራስህ በጥነንቃቄ ምራው..ምንም ችግር እንዲፈተረር አልፈልግም.እናም ደግመ ማንኛቸውም እንዳይጎዱ›
የፕሮፌሰሩ መልዕክተኛ ከፕሮፌሰሩu ጋር አያወራ የነበረው ከመኪናው ወጥ ገቢናውን ተደግፎ ነበር..አውርቶ ከጨረሰ ብሃላ እንደታዘው መኪናዋን ለመከተል ወደመኪናው ሊገባ ሲል ከኃላው ማጀራቱ ላይ ቀዝቀቃዛ ብረት አረፈ..ሊዞር ሲል
‹‹ቀጥ ብለህ ባለህበት ቁም››የሚል ድምፅ አስጠነቀቀው…እንደተባለው አደረገ፡፡.ትዘዛዙን አክብሮ ገባና የሹፌሩን ቦታ ያዘ..ሌለኛው ዞሮ ገባና ከጎኑ ተቀመጠ…ሽጉጥ የደቀነው በጥንቃቄ የሃላውን በራፍ ከፍቶ ገባ…ሽጉጡን በጭንቅላቱ አስተካክሎ አንደቀነበት ነው፡ገቢና ከጎኑ ያለው ዘና ብሎ ስልክ አውጥቶ ደወለ..
‹ሄሎ ስንደርስ ይዛዋት ሄደዋል .ግን አንድ የእነሱን ሰው ከነመኪናው ይዘነዋ… ምን እናድርገው?፡፡›ታጋቹ እንዲሰማው ሞባይሉን ላውድ ላይ አደረገ…
‹‹ከፈለጋችሁ ሰባብሩት..ካልሆነም ቆራርጡትና ቀጥታ ወደ ወሰዷት ቦታ እንዲመራችሁ አድርጉ፡፡እነአቤሎም ወደ እናተ እንዲመጡ አ,እና እንዲያግዛችሁ አደርጋለው … እኔም መጣሁ››ስልኩ ተዘጋ፡
‹ሀለቃችን ያለውን ሰምተሀል አይደል?፡፡›
‹አዎ ሰምቼያለው…..››
‹‹ስለዚህ እነደማይ አንተም እንደ እኛ ባለሞያ ነህ… ስለዚህ ከአንተ ጠብ የለንም…ጓደኞችህ ወደየት ነው የወሰዶቸው?››
‹‹አልገባችሁም..ሰዎቹ ጎደኞቼ አይደሉም…በእርግጥ እኔ ፕሮፌሰሩ ሂድና አምጣት ብሎኝ ነበር የመጣሁት…እራሷ ደውላ ውሰደኝ ስላለችው ኃይል ና ግርግር ስለማያስፈልግ ብቻዬን ነበር የመጣሁት፡፡ ስደርስ ግን አራት የታጠቁና የተደራጁ አፋኞች መኪናዋ ውስጥ ሲከቷት ደረስኩ፡፡ለሀለቃዬ ደውዬ ስነግረው ተከተላቸውና የገቡበትን እይ ብሎኝ ነበር..›
‹‹እናስ?›
‹‹እናማ እናንተ አሰናከላችሁኝ ..››
‹እስኪ ፍጠን ሞተሩን አስነሳው..በየት ነው የሄዱት፣በፊት ለፊት ሄደው ማደያው ጋ ሲደርሱ ወደግራ ነው የታጠፉት…››
‹ንዳው.ንዳው›ጮኸበት፡፡
መዳው.. ወደግራ ታጠፉ ፡፡አንድ ኪሎ ሜትር ያህል ዙሪያ ገባቸውን እቃኙ ቢበሩም የተባለችውን መኪና ሊያገኞት አልቻሉም…
መልሶ ደወለለት…ለአብዬት…ያለውን ነገረው..፡፡
‹‹እወነቱን ከሆነ ፕሮፌሰሩ ጋር ይውሰዳችሁ….አሳልፎ ይስጣችሁ እሱን ይዛችሁልኝ ኑ..››
‹‹እሺ››
‹‹ነግሬሀለው ስህተት አልፈልግም..ወይ ዶክተሯንና ካሳን ወይም ደግሞ ፕሮፌሰሩን አሁኑኑ ፈልጋለው..››ስልኩ ተዘጋ
‹‹ያው የስራውን አካሄድ ምታውቅው ነው…አንተ ላይ ብጢ መሰንዘር ወይ ደግሞ ተኩሶ ተፋህን መበርቀስ አልፈልግም…..ካልሆነ ግን
‹‹ጓደኛዬ ላይም ሆነ እኔ ላይ ምንም አደጋ እንዲደርስ አልፈልግም››መለሰ
‹‹ነገርኩህ እኮ..እንደው ቀልል እንዲል ካደረጋችሁ ለሀለቃችን በማስረዳ ከዚህ ያጣችሁትን ስራ እኛ ጋር እንድታገኙ ማድረግ እንችላለን፡፡
👍29
‹‹ችግር የለውም…ከሰውዬው ጋ እኮ ገና ዛሬ ነው ስራ የጀመርነው…››
ስለዚህ ወደእዛው ንዳው…ላስጠንቅቅህ.ምንም አይንት የማታል ወይ የማጭበርበር ሙከራ ለሞከር እንደታስብ››
ተስማማና ወደፕሮፌሰሩ ቤት መንዳት ጀመረ. . መንገድ ላይ ሌላ ሁለት ጓደኞቻቸውን ጨምረው አራት ሆነው ፕሮፌሰሩ የተደበቀበት ቤት ደረሱ….ጠቅላላ ኦፕሬሽኑ 15 ደቂቃ ነው የፈጀው….ሲደርሱ ጠባቂዎቹ ዶክተሯን የወሰደውን መኪና ለማግኘት ተሰማርተው ስለነበረ ከዘበኛው በስተቀር ሌላ ጠባቂ አልነበረውም..ዘበኛውን ደግሞ ሰብለ በአንድ ጥፊ ነው ዝም እንዲል ያደረገችው ፡፡ ከቤቱ አውጥተው መኪናቸው ውስጥ ጨመረው ይዘውት እየሄዱ ነው፡፡
ፕሮፌሰሩ መንገዱን ሙሉ እየለፈለፈፈ ነበር‹‹ለባለስልጣኖቹ ሀለቆቻችሁ ንገሯቸው…ካለቀልኝ ያልቅላቸዋል..እኔን ማሳፈን ቀላል እንዳልሆነ አልገባቸውም›› ስላስቸገራቸው በአፉ ጨርቅ ጠቅጥቀው አሰሩት፡፡
እንደደረሰ ሰሎን አስገብተው አብዬት ፊት ሲያቆሙት ደነገጠ…በፍፅም ያልጠረጠረው ተአምር ነው..ይንን ሰው በፎቶ እነዶዬ አሳይተውታል…ዶክተሯን ይረዳታል የተባለው ሰውዬ ነው…በአካል ሲያየው በዝና ከሰማውና በፎቶ ባየው ጊዜ ከፈራው በላይ ፈራ፡፡አብዬት ፐሮፌሰሩን አንገቱን አንቆ ወደፎቅ ይዞት ወጣና አንድ ባዶ ክፍል ውስጥ ወረወረው፡፡በራፉን በላው ላይ በመዝጋት ቀርቅሮበት ወደ መሳሪያ ማከማቻ ክፍል ሄደና ሚፈልጋቸውን መሳሪያዎች ሰበሰቦ ተመለሰ.. ፕሮፌሰሩን ወደአስቀመጠበት ክፍል ገባና ፊቱ ለፊቱ ደረደራቸው….፡፡
‹‹የት ነች ያለችው?››
‹‹በእውነት በፈለከው ነገር እምልልሀለው የት እንዳች አላውቅም፡፡››ፕሮፌሰሩ የወላጆቹን ዱላ ፈርቶ እንደሚሽቆጠቆጥ ህፃን ልጅ ተርበተበተ
‹‹አንተን ልታገኝ ነበር የመጣችው…››
‹አዎ ደውላልኝ ካንተ ጋር ማውራት ፈልጋለሁ አለቺኝ….እሺ ብዬ መኪናና ሺፌር ላኩላት…ሹፌሩ ሲደርስ የሆኑ ሰዎች እያፈኗት ነበር….ሹፌሩ ሲነግረኝ.ተከተልና አድናት ብዬው ነበር….ከዛ ብኃላ የሆነውን አላውቅም.››…
አይዞህ እንድታውቅ አደርጋለው..አለና ከጩቤዎች መካከል አንዱን መዘዘና እያገለባበጠ ወደእሱ ተጠጋ..ፕሮፌሰሩ አይኖቹን አጉረጠረጠ…. አብዬት ድንገት ወደምድር ቁጢጥ አለና ጩቤውን ግራ እግሩ ላይ ሰካው…ጩቤው በጫማው አልፎ እግሩ ላይ ተሰነቀረ….ፕሮፌሰሩ አጓራና መሬት ላይ ተዘረረ…
‹‹ምን እያደረክ ነው…?ምትፈልገውን ነገር በሰላም አትጠይቀኝም….?ምን አይነት ጭካኔ ነው?››ለሀጩን እያዝረከረከ ለፈለፈ.
‹‹እሺ አሁን እራስህን ታረጋጋለህ ወይስ ልድገመው…?››
‹‹አረ በፈጠረህ፣ግፍ አትፈራም…?››
‹‹እሺ እንግዲህ እንድደግመው ካልፈለክ….አሁን እራስህን አረጋጋና ዶዬህ ጋ ደውል››
‹‹ዶዬ ማን ነው?››
‹‹ነው ልድገመው ማለት ነው›› አለና ሲጠጋ
‹‹አይ ማለቴ ዶዬ እዚህ የለም ብዬ ነው››
‹‹እኮ እኔም እኮ አለ አላልኩም..ደውልለትና የዶክተሯን ቤተሰቦች እቤታቸው በክብር ተንከባክቦ ይመልሳቸውና ቀጥታ በቪዲዬ ያረጋግጥልኝ፡፡
‹‹ስልኬን እቤት ጥዬ ነው የመጣሁት....ቁጥሩን አላውቅም››
‹‹ግድ የለም….››ስልኩን አወጣና ደወለ…ለፕሮፌሰሩ አቀበለው..የተባውን መልዕክት ያለምንም ዝንፈት ፈፀመ ….
‹‹አብዬት ለዶዬ ደወለለት..››
‹‹አቤት አብዬት››
‹‹ጦርነቱ ከእናንተ ጋር አይደለም፡፡››
‹ነው እንጂ…ፕሮፌሰሩ ለህግ ፊት ከቀረበ እኛን አሳልፎ የማይሰጠን ይመስልሀል››
‹‹ስለዚህ አግዙኝ ላግዛችሁ››
‹‹ምንድነው ምናግዝገህ?››
እንደምታውቁት እኔ ፕሮፌሰሩን ይዤዋለው..ሙሉ የሚባለውንም አጋሩን በእጄ ገብቶ አሁን ይዘውት እየመጡ ነው…..ዶክተሯን እና አንድ ጓደኛችንን ደግሞ ማን እንደጠለፋቸው አናውቅም….እንሱን እንዳገኝ ከረዳችሁኝ..እኔም ወደእናንተ ሚጠቁም ማንኛውንም የማገኘውን መረጃ ላጠፋላችሁ ቃል እገባለው፡፡
‹‹በቃ አሁን ወደአዲስ አበባ ለመምጣ ከጎንደር ከተማ እየወጣን ነው..ነገ እንደገባን እንገናኝና በጉዳዩ እንወያይ››
‹‹ዶዬ…ታውቀኛለህ እኔ አብዬት ነኝ….በአካል አንገናኝም….በስልክ እስከፈለከው እናወራለን..ደግሞ የገባሁትን ቃል መቼም እንደማላጥፍ ታውቃላችሁ..እናንተም እንደምታከብሩ አውቃለሁ….ጓደኞቼን እንዳገኝ እርዱኝ እኔም እንዳልኩት አደርጋለሁ››
‹‹እሺ አቢ…እንዳልክ ይሆናል እናመሰግናለን…..››
‹‹ምንም አይደል፡፡››
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
ስለዚህ ወደእዛው ንዳው…ላስጠንቅቅህ.ምንም አይንት የማታል ወይ የማጭበርበር ሙከራ ለሞከር እንደታስብ››
ተስማማና ወደፕሮፌሰሩ ቤት መንዳት ጀመረ. . መንገድ ላይ ሌላ ሁለት ጓደኞቻቸውን ጨምረው አራት ሆነው ፕሮፌሰሩ የተደበቀበት ቤት ደረሱ….ጠቅላላ ኦፕሬሽኑ 15 ደቂቃ ነው የፈጀው….ሲደርሱ ጠባቂዎቹ ዶክተሯን የወሰደውን መኪና ለማግኘት ተሰማርተው ስለነበረ ከዘበኛው በስተቀር ሌላ ጠባቂ አልነበረውም..ዘበኛውን ደግሞ ሰብለ በአንድ ጥፊ ነው ዝም እንዲል ያደረገችው ፡፡ ከቤቱ አውጥተው መኪናቸው ውስጥ ጨመረው ይዘውት እየሄዱ ነው፡፡
ፕሮፌሰሩ መንገዱን ሙሉ እየለፈለፈፈ ነበር‹‹ለባለስልጣኖቹ ሀለቆቻችሁ ንገሯቸው…ካለቀልኝ ያልቅላቸዋል..እኔን ማሳፈን ቀላል እንዳልሆነ አልገባቸውም›› ስላስቸገራቸው በአፉ ጨርቅ ጠቅጥቀው አሰሩት፡፡
እንደደረሰ ሰሎን አስገብተው አብዬት ፊት ሲያቆሙት ደነገጠ…በፍፅም ያልጠረጠረው ተአምር ነው..ይንን ሰው በፎቶ እነዶዬ አሳይተውታል…ዶክተሯን ይረዳታል የተባለው ሰውዬ ነው…በአካል ሲያየው በዝና ከሰማውና በፎቶ ባየው ጊዜ ከፈራው በላይ ፈራ፡፡አብዬት ፐሮፌሰሩን አንገቱን አንቆ ወደፎቅ ይዞት ወጣና አንድ ባዶ ክፍል ውስጥ ወረወረው፡፡በራፉን በላው ላይ በመዝጋት ቀርቅሮበት ወደ መሳሪያ ማከማቻ ክፍል ሄደና ሚፈልጋቸውን መሳሪያዎች ሰበሰቦ ተመለሰ.. ፕሮፌሰሩን ወደአስቀመጠበት ክፍል ገባና ፊቱ ለፊቱ ደረደራቸው….፡፡
‹‹የት ነች ያለችው?››
‹‹በእውነት በፈለከው ነገር እምልልሀለው የት እንዳች አላውቅም፡፡››ፕሮፌሰሩ የወላጆቹን ዱላ ፈርቶ እንደሚሽቆጠቆጥ ህፃን ልጅ ተርበተበተ
‹‹አንተን ልታገኝ ነበር የመጣችው…››
‹አዎ ደውላልኝ ካንተ ጋር ማውራት ፈልጋለሁ አለቺኝ….እሺ ብዬ መኪናና ሺፌር ላኩላት…ሹፌሩ ሲደርስ የሆኑ ሰዎች እያፈኗት ነበር….ሹፌሩ ሲነግረኝ.ተከተልና አድናት ብዬው ነበር….ከዛ ብኃላ የሆነውን አላውቅም.››…
አይዞህ እንድታውቅ አደርጋለው..አለና ከጩቤዎች መካከል አንዱን መዘዘና እያገለባበጠ ወደእሱ ተጠጋ..ፕሮፌሰሩ አይኖቹን አጉረጠረጠ…. አብዬት ድንገት ወደምድር ቁጢጥ አለና ጩቤውን ግራ እግሩ ላይ ሰካው…ጩቤው በጫማው አልፎ እግሩ ላይ ተሰነቀረ….ፕሮፌሰሩ አጓራና መሬት ላይ ተዘረረ…
‹‹ምን እያደረክ ነው…?ምትፈልገውን ነገር በሰላም አትጠይቀኝም….?ምን አይነት ጭካኔ ነው?››ለሀጩን እያዝረከረከ ለፈለፈ.
‹‹እሺ አሁን እራስህን ታረጋጋለህ ወይስ ልድገመው…?››
‹‹አረ በፈጠረህ፣ግፍ አትፈራም…?››
‹‹እሺ እንግዲህ እንድደግመው ካልፈለክ….አሁን እራስህን አረጋጋና ዶዬህ ጋ ደውል››
‹‹ዶዬ ማን ነው?››
‹‹ነው ልድገመው ማለት ነው›› አለና ሲጠጋ
‹‹አይ ማለቴ ዶዬ እዚህ የለም ብዬ ነው››
‹‹እኮ እኔም እኮ አለ አላልኩም..ደውልለትና የዶክተሯን ቤተሰቦች እቤታቸው በክብር ተንከባክቦ ይመልሳቸውና ቀጥታ በቪዲዬ ያረጋግጥልኝ፡፡
‹‹ስልኬን እቤት ጥዬ ነው የመጣሁት....ቁጥሩን አላውቅም››
‹‹ግድ የለም….››ስልኩን አወጣና ደወለ…ለፕሮፌሰሩ አቀበለው..የተባውን መልዕክት ያለምንም ዝንፈት ፈፀመ ….
‹‹አብዬት ለዶዬ ደወለለት..››
‹‹አቤት አብዬት››
‹‹ጦርነቱ ከእናንተ ጋር አይደለም፡፡››
‹ነው እንጂ…ፕሮፌሰሩ ለህግ ፊት ከቀረበ እኛን አሳልፎ የማይሰጠን ይመስልሀል››
‹‹ስለዚህ አግዙኝ ላግዛችሁ››
‹‹ምንድነው ምናግዝገህ?››
እንደምታውቁት እኔ ፕሮፌሰሩን ይዤዋለው..ሙሉ የሚባለውንም አጋሩን በእጄ ገብቶ አሁን ይዘውት እየመጡ ነው…..ዶክተሯን እና አንድ ጓደኛችንን ደግሞ ማን እንደጠለፋቸው አናውቅም….እንሱን እንዳገኝ ከረዳችሁኝ..እኔም ወደእናንተ ሚጠቁም ማንኛውንም የማገኘውን መረጃ ላጠፋላችሁ ቃል እገባለው፡፡
‹‹በቃ አሁን ወደአዲስ አበባ ለመምጣ ከጎንደር ከተማ እየወጣን ነው..ነገ እንደገባን እንገናኝና በጉዳዩ እንወያይ››
‹‹ዶዬ…ታውቀኛለህ እኔ አብዬት ነኝ….በአካል አንገናኝም….በስልክ እስከፈለከው እናወራለን..ደግሞ የገባሁትን ቃል መቼም እንደማላጥፍ ታውቃላችሁ..እናንተም እንደምታከብሩ አውቃለሁ….ጓደኞቼን እንዳገኝ እርዱኝ እኔም እንዳልኩት አደርጋለሁ››
‹‹እሺ አቢ…እንዳልክ ይሆናል እናመሰግናለን…..››
‹‹ምንም አይደል፡፡››
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍40❤5
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ
ከፖርት ፕሪንስ በስተ ምስራቅ ፓርቶሪኮ ሳንጁአን ውስጥ የግል እርሻ የጀመረው አሌክስ ቀደም ሲል የስፔን ፋሽዝም
አራማጅና የጦር አባል ከነበረው ስመ ጥር አባቱ ጋር ወደ ፓርቶሪ
በተደጋጋሚ ከሄደ በኋላ ሳንጁአን ለመኖር እንዲወስን ተፈጥሮአዊ
ፍቅሩ አደፋፈረው፡
የሻምበልነት ማዕረግ የነበረው አባቱ ልጁ በእርሻ ትምህርት ሰልጥኖ ህይወቱ በእርሻ ምርት ላይ ቢመሰረት የወደፊት ዕድሉ
የተቃና ደስተኛና ሃብታም ሊሆን እንደሚችል በመከረው መሰረት
አሴክስ የአባቱን ህልም የእራሱ በማድረግ ህልሙን ለማሳካት የሚያስችለውን ጥረት ፈጽሞ በመጨረሻ ተሳካለት፡
አሌክስ ደጋግሞ ስለ እርሻ ዘመናዊ እርሻ ስለሚያስገኘው
ብልፅግና ስለ ተሻሉ የምርት ውጤቶች ማውራት እንጂ በፍቅሩ ተረትታ
እንደነፍስ ጡር ለምትብረከረከው
ፍቅረኛው ቁብ
አልነበረውም ሌላው ቀርቶ እግሩ ስር እንደምትታከከውና "ፔሙስ" ብሎ እንደሚጠራት ድመቱ ሲገናኙ እጁን ሰዶ ዳብሷት ካልያም እጆችዋን ስቦ ወደ ደረቱ አስጠግቷት አያውቅም አይብዛ እንጂ
አንድ ወቅት የፍቅር አባባሎችን ይለዋወጡ አብረውም እየተሻሹ
ጊዜያቸውን በደስታ ያሳልፉ የነበረ ቢሆንም! ያ የስሜት መመሳሰል ግን ከጠለቀ ብዙ ወራቶች ተቆጠሩ።
ይህ የቸልተኝነት ባህሪው ሸበላ ቁመናው የታከታት ደረቅ የአጨዋወት ስልቱ ሳይቀር አኜስን ለአሌክስ ያላትን ስሜት ከእለት
ወደ እለት እንዲያድግ አደረገው። አንዳንዴ እንዲያውም፡-
“አሌክስ! እባክህ ለፍቅራችን የሚሆን ጊዜ ይኑርህ? እባክህ በፍቅር
ስሜቴ አትጫወትበት!...” በማለት ምርር ብላ ስትነግረው፡-
“እባክሽ አኜስ ታገሽ!
ትዕግስት ይኑርሽ! ልትረጅኝ
ሞክሪ! በአሁኑ ሰዓት የፍቅር ስሜቴ በወደፊት ዓላማዬ እንደ ጉም ተሸፍኗል። አንድ ወቅት ግን ጉሙ ይበተናል፤ በሰማያዊው ሰማይ
ከምስራቅ ወደ ምዕራብ እንደምትጓዝ ፀሐይ የፍቅር ብርሃን ፍንትው ብሎ ይፈነጥቃል...'' ይላታል:
“አሌክስ! እኔ'ኮ ብዙ ላሳስብህ አልሻም። በሳምንት ቢያንስ
ለተወሰነ ደቂቃ እንኳ ፍቅር እንድንለዋወጥ ለማድረግ ሞክር ፧እየተጎዳሁ ነው” ስትለው፡-
“እስኪ እሞክራለሁ አንች ግን ጠንከር በይ: በህልሜ
ልትደሰች ሞክሪ በአትላንቲክ ውቅያኖስ በተከበበችው ሳን ጁን
ውስጥ የሚኖረው ቡቃያ ንፋሱ ጎንበስ ቀና ሲያደርገው ይታይሽ!
አዲዎስ ብሏት ይሄዳል።
አንድ ቀን ግን አሌክስ በጅፕ መኪናው መኖሪያዋ ድረስ መጥቶ ድንገት “ለሽርሽር እንሂድ? አላት።
“የት?” አለችው አኜስ ግራ ተጋብታ።
“ሱ..” አለ አፉን በቀኝ እጁ አመልካች ጣት እየጠበጠበ።
“አሌክስ የት እንደምንሄድ መንገሩን ባትፈልግ እንኳን ወጣ እንደምንል ቀደም ብለህ ፍንጭ መስጠት ነበረብህ: ከሰዓታት
ወይንም ከቀናት በፊት ወጣ እንደምንል ነግረኸኝ ቢሆን ኖሮ ነፍሴ በደስታ ከመዝለሏም በተጨማሪ ስሜቴ በጉጉት ተበረጋግዶ በናፍቆት ይጠብቅህ ነበር: አሁን ግን ልቤ በሐዘን ቀዝቅዛለች። ስሜቴም በድን
ነው። እኔም ስላልተዘጋጀሁ የትም መሄድ አልፈልግም” አሰችው።
ያልተለመደ ፈገግታ አሳይቶ ባልጠበቀችው መልክ የግራ እጅዋን ብድግ አድርጎ ጣቶችዋን ሳም ሳም አደረጋት፤ ጉንጯን በቀኝ
እጅ አመልካች ጣቱ ደባበሰላት: ሽቅብ አንስቶም ከንፈሯን በከንፈሩ
ደባበሰላት።
ወዲያው ልቧ ጋለች ሰውነቷ በሙቀት ተጥለቀለቀ፡
የፍቅር ሃይሏ ከየስርቻው ተሰባሰበ ስለዚህ! “ማሬ!
እንሂድ" አለችው::ሃሳቡን እንዳይለወጥ እየሰጋች: አሌክስ መኪናውን እያሽከረከረ ጭኖችዋን በቀኝ እጁ እየደባበሰ የምትሆነውን አሳጣት: ያ ጨካኙ አሌክስ ሳይሆን የፍቅር መልአክ ሆነባት…
“አሌክስ አልቻልሁም አለችው እየተስለመለመች
ጥቂት ኪሎ ሜትር እንደተጓዙ።
“ትዕግስት ጥሩ ነው..."
“ኡፍ ስብከትህን አቁም። በሰዎች ሙያ ጣልቃ አትግባ መኪናዋን ይልቁንስ አቁም አለችው በትዕዛዝ መልክ፡ መኪናዋ ወደ
ዳር ወጥታ ቆመች ሞተሯ ጠፋ።
ከተቀመጠችበት ዞር ብላ እጆችዋን ዘርግታ የአሌክስን
አንገት አቀፈችው። ተገናኙ
ረሃብተኛዋ ከንፈሩን ጎረሰቸው እፅዋት በነፋሱ ጎንበስ ቀና ይላሉ ከርቤው እየጤሰ መላዕክት
እያጀቧቸው ሽቅብ በፍቅር ስረገላ አረጉ።
“አሌክስ! እኔ አላምንም... እንዴት ደስ አለኝ ለካ እንዲህ የደስታ ምንጭ ነህ እሰይ እንኳን ታገስኩህ እንኳን ቻልኩህ እንግዲህ ዳግመኛ ከፍቅር ሠረገላችን አንወርድም አይደል! ከምድር ላይ ይልቅ እዚህ ነፍስ ነህ..." እያለች ላዩ ላይ ተንከባለለችበት
የአትላንቲክ ውቅያኖስ ማዕበል በርቀት ከቆሙት መርከቦችና አጠገባቸው ካለው የድንጋይ ግንብ ጋር እየተላተመ አረፋ ሲደፍቅ
ከኮሎምበስ መታሰቢያ ግዙፍ ሃውልት ትይዩ የሚነፍሰው ጤሮ ንፋስ በጆሮ ግንዷ እያፋጨ ሲያልፍ ግን አይኗን ገልጣ ከገነት ወደ ምድር ተመለሰች። ምድሯን ውቅያኖሱን ስታይ አስጠሏት፡ አሌክስ
አሁንም አብሯት አለ ያ ሲያደርጉ የነበረውና አሁን አጠገቧ ባለው አሌክስ መካከል ግን ልዩነት ያለ መሰላት፤ ተጠራጠረችው።
“ማሬ የት ነው ያለነው?" ከሰመመኗ እንደነቃች ጠየቀችው።
“ሁዌልቫ ነን! ለስንብት አመች በመሆኗ የምሄድበትንም ከርቀት ላሳይሽ ስለምችል ሁዌልቫን መርጨልሻለሁ" አላት ሳብ አድርጎ ወርቃማ ዞማ ፀጉሯን ስሞ፡
“ሁዌልቫ” ይህ ስም ምድር ላይ ያውም ስፔን ውስጥ
የምታውቃት ከተማ ስም ነው:
“ለምን ግን እዚህ አመጣኸኝ?” ተሸበረች:
“ለስንብት አልሁሽ እኮ! አላት ወደ እሱ ጠጋ አድርጎ
እያቀፋት ሰውነቱ ሰውነቷን ሲነካት እየዘገነናት
“የምን ስንብት?... ደግሞ እንዴት ጨካኝ ነህ?... በአንዴ ከደስታ ወደ መከራ ትመልሰኝ..." አለችና ልሳኗ ተዘጋ: አሌክስ ሲስማት ከንፈሯ እንደ በረዶ ቀዘቀዛት።
ዙሪያቸውን እንደ እንቦቀቅላ ህፃን ድክ ድክ የሚሉት
እርግቦች አንዳች ነገር እንደመጣባቸው ሁሉ ድንገት ግር ብለው ወደ
ሃይቁ አቅጣጫ በረሩ።
አኜስ የአሌክስን እጆች ወርውራ እርግቦችን
ተመለከታቸው።
እጥፍ ብለው እንደገና ሽቅብ ጎነው በረሩ: አሌክስ ፊቷን ወደ እሱ አዙሮ
“ሰርቶ መበልፀግ ስመኘው የኖርሁትን እድል በማግኘቴ
ረክቻለሁ። ፍቅራችን ከብልፅግና ማግስት.. ጆሮዋ ደነቆረ: ከዚያ በኋላ የሚለውን አልሰማችውም።
ፍቅር ከብልፅግና
ማግስት…" አባባሉ በአእምሮዋ አስተጋባ:
ዛሬን አበላሽቶ ነገን ማስዋብ ፍቅርን ገፍትሮ ጥቅምን ማቀፍ
ተምታታባት እሪ ብለሽ ጩሂ አሰኛት… መጮህ ግን ተሳናት::ለመጮሀም ኃይል ያስፈልጋል።
አሌክስን ጠላችው 1
ገፋችው... ከዚያ እርግቦቹ ወደ ሄዱበት አቅጣጫ በረረች “አዕዋፍ ለካ ወደው ከምድር ርቀው አይበሩም ብላ በአየር ላይ ለመብረር ወደ ሰማዬ ሰማያት ለመጎን ሞከረች ትናንሽ ፍጡራን የፈፀሙትን ግን መፈፀም ተሳናት።
ይህ ከሆነና ከአሌክስ በተለየች በአምስት ዓመቷ “አሽቀንጥሬ ጣልሁት ያለችው የከንፈር ወዳጅዋ አንደገና ራባት። ፍቅሩ አገርሽቶ ጤና አሳጣት ስለዚህ ፓርቶሪኮን ለመጎብኘት በሚል ሽፋን ወደ ሳንጁአን ሄደች።
ሳን ጁአን እንደደረስችም አሌክስ በሰጣት የእርሻ ጣቢያ ማዕከል አዳራሻ ሄዳ አሌክስን እንዲያገናኝዋት ጠየቀች። በእርግጥ
፡
፡
#ክፍል_አስር
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ
ከፖርት ፕሪንስ በስተ ምስራቅ ፓርቶሪኮ ሳንጁአን ውስጥ የግል እርሻ የጀመረው አሌክስ ቀደም ሲል የስፔን ፋሽዝም
አራማጅና የጦር አባል ከነበረው ስመ ጥር አባቱ ጋር ወደ ፓርቶሪ
በተደጋጋሚ ከሄደ በኋላ ሳንጁአን ለመኖር እንዲወስን ተፈጥሮአዊ
ፍቅሩ አደፋፈረው፡
የሻምበልነት ማዕረግ የነበረው አባቱ ልጁ በእርሻ ትምህርት ሰልጥኖ ህይወቱ በእርሻ ምርት ላይ ቢመሰረት የወደፊት ዕድሉ
የተቃና ደስተኛና ሃብታም ሊሆን እንደሚችል በመከረው መሰረት
አሴክስ የአባቱን ህልም የእራሱ በማድረግ ህልሙን ለማሳካት የሚያስችለውን ጥረት ፈጽሞ በመጨረሻ ተሳካለት፡
አሌክስ ደጋግሞ ስለ እርሻ ዘመናዊ እርሻ ስለሚያስገኘው
ብልፅግና ስለ ተሻሉ የምርት ውጤቶች ማውራት እንጂ በፍቅሩ ተረትታ
እንደነፍስ ጡር ለምትብረከረከው
ፍቅረኛው ቁብ
አልነበረውም ሌላው ቀርቶ እግሩ ስር እንደምትታከከውና "ፔሙስ" ብሎ እንደሚጠራት ድመቱ ሲገናኙ እጁን ሰዶ ዳብሷት ካልያም እጆችዋን ስቦ ወደ ደረቱ አስጠግቷት አያውቅም አይብዛ እንጂ
አንድ ወቅት የፍቅር አባባሎችን ይለዋወጡ አብረውም እየተሻሹ
ጊዜያቸውን በደስታ ያሳልፉ የነበረ ቢሆንም! ያ የስሜት መመሳሰል ግን ከጠለቀ ብዙ ወራቶች ተቆጠሩ።
ይህ የቸልተኝነት ባህሪው ሸበላ ቁመናው የታከታት ደረቅ የአጨዋወት ስልቱ ሳይቀር አኜስን ለአሌክስ ያላትን ስሜት ከእለት
ወደ እለት እንዲያድግ አደረገው። አንዳንዴ እንዲያውም፡-
“አሌክስ! እባክህ ለፍቅራችን የሚሆን ጊዜ ይኑርህ? እባክህ በፍቅር
ስሜቴ አትጫወትበት!...” በማለት ምርር ብላ ስትነግረው፡-
“እባክሽ አኜስ ታገሽ!
ትዕግስት ይኑርሽ! ልትረጅኝ
ሞክሪ! በአሁኑ ሰዓት የፍቅር ስሜቴ በወደፊት ዓላማዬ እንደ ጉም ተሸፍኗል። አንድ ወቅት ግን ጉሙ ይበተናል፤ በሰማያዊው ሰማይ
ከምስራቅ ወደ ምዕራብ እንደምትጓዝ ፀሐይ የፍቅር ብርሃን ፍንትው ብሎ ይፈነጥቃል...'' ይላታል:
“አሌክስ! እኔ'ኮ ብዙ ላሳስብህ አልሻም። በሳምንት ቢያንስ
ለተወሰነ ደቂቃ እንኳ ፍቅር እንድንለዋወጥ ለማድረግ ሞክር ፧እየተጎዳሁ ነው” ስትለው፡-
“እስኪ እሞክራለሁ አንች ግን ጠንከር በይ: በህልሜ
ልትደሰች ሞክሪ በአትላንቲክ ውቅያኖስ በተከበበችው ሳን ጁን
ውስጥ የሚኖረው ቡቃያ ንፋሱ ጎንበስ ቀና ሲያደርገው ይታይሽ!
አዲዎስ ብሏት ይሄዳል።
አንድ ቀን ግን አሌክስ በጅፕ መኪናው መኖሪያዋ ድረስ መጥቶ ድንገት “ለሽርሽር እንሂድ? አላት።
“የት?” አለችው አኜስ ግራ ተጋብታ።
“ሱ..” አለ አፉን በቀኝ እጁ አመልካች ጣት እየጠበጠበ።
“አሌክስ የት እንደምንሄድ መንገሩን ባትፈልግ እንኳን ወጣ እንደምንል ቀደም ብለህ ፍንጭ መስጠት ነበረብህ: ከሰዓታት
ወይንም ከቀናት በፊት ወጣ እንደምንል ነግረኸኝ ቢሆን ኖሮ ነፍሴ በደስታ ከመዝለሏም በተጨማሪ ስሜቴ በጉጉት ተበረጋግዶ በናፍቆት ይጠብቅህ ነበር: አሁን ግን ልቤ በሐዘን ቀዝቅዛለች። ስሜቴም በድን
ነው። እኔም ስላልተዘጋጀሁ የትም መሄድ አልፈልግም” አሰችው።
ያልተለመደ ፈገግታ አሳይቶ ባልጠበቀችው መልክ የግራ እጅዋን ብድግ አድርጎ ጣቶችዋን ሳም ሳም አደረጋት፤ ጉንጯን በቀኝ
እጅ አመልካች ጣቱ ደባበሰላት: ሽቅብ አንስቶም ከንፈሯን በከንፈሩ
ደባበሰላት።
ወዲያው ልቧ ጋለች ሰውነቷ በሙቀት ተጥለቀለቀ፡
የፍቅር ሃይሏ ከየስርቻው ተሰባሰበ ስለዚህ! “ማሬ!
እንሂድ" አለችው::ሃሳቡን እንዳይለወጥ እየሰጋች: አሌክስ መኪናውን እያሽከረከረ ጭኖችዋን በቀኝ እጁ እየደባበሰ የምትሆነውን አሳጣት: ያ ጨካኙ አሌክስ ሳይሆን የፍቅር መልአክ ሆነባት…
“አሌክስ አልቻልሁም አለችው እየተስለመለመች
ጥቂት ኪሎ ሜትር እንደተጓዙ።
“ትዕግስት ጥሩ ነው..."
“ኡፍ ስብከትህን አቁም። በሰዎች ሙያ ጣልቃ አትግባ መኪናዋን ይልቁንስ አቁም አለችው በትዕዛዝ መልክ፡ መኪናዋ ወደ
ዳር ወጥታ ቆመች ሞተሯ ጠፋ።
ከተቀመጠችበት ዞር ብላ እጆችዋን ዘርግታ የአሌክስን
አንገት አቀፈችው። ተገናኙ
ረሃብተኛዋ ከንፈሩን ጎረሰቸው እፅዋት በነፋሱ ጎንበስ ቀና ይላሉ ከርቤው እየጤሰ መላዕክት
እያጀቧቸው ሽቅብ በፍቅር ስረገላ አረጉ።
“አሌክስ! እኔ አላምንም... እንዴት ደስ አለኝ ለካ እንዲህ የደስታ ምንጭ ነህ እሰይ እንኳን ታገስኩህ እንኳን ቻልኩህ እንግዲህ ዳግመኛ ከፍቅር ሠረገላችን አንወርድም አይደል! ከምድር ላይ ይልቅ እዚህ ነፍስ ነህ..." እያለች ላዩ ላይ ተንከባለለችበት
የአትላንቲክ ውቅያኖስ ማዕበል በርቀት ከቆሙት መርከቦችና አጠገባቸው ካለው የድንጋይ ግንብ ጋር እየተላተመ አረፋ ሲደፍቅ
ከኮሎምበስ መታሰቢያ ግዙፍ ሃውልት ትይዩ የሚነፍሰው ጤሮ ንፋስ በጆሮ ግንዷ እያፋጨ ሲያልፍ ግን አይኗን ገልጣ ከገነት ወደ ምድር ተመለሰች። ምድሯን ውቅያኖሱን ስታይ አስጠሏት፡ አሌክስ
አሁንም አብሯት አለ ያ ሲያደርጉ የነበረውና አሁን አጠገቧ ባለው አሌክስ መካከል ግን ልዩነት ያለ መሰላት፤ ተጠራጠረችው።
“ማሬ የት ነው ያለነው?" ከሰመመኗ እንደነቃች ጠየቀችው።
“ሁዌልቫ ነን! ለስንብት አመች በመሆኗ የምሄድበትንም ከርቀት ላሳይሽ ስለምችል ሁዌልቫን መርጨልሻለሁ" አላት ሳብ አድርጎ ወርቃማ ዞማ ፀጉሯን ስሞ፡
“ሁዌልቫ” ይህ ስም ምድር ላይ ያውም ስፔን ውስጥ
የምታውቃት ከተማ ስም ነው:
“ለምን ግን እዚህ አመጣኸኝ?” ተሸበረች:
“ለስንብት አልሁሽ እኮ! አላት ወደ እሱ ጠጋ አድርጎ
እያቀፋት ሰውነቱ ሰውነቷን ሲነካት እየዘገነናት
“የምን ስንብት?... ደግሞ እንዴት ጨካኝ ነህ?... በአንዴ ከደስታ ወደ መከራ ትመልሰኝ..." አለችና ልሳኗ ተዘጋ: አሌክስ ሲስማት ከንፈሯ እንደ በረዶ ቀዘቀዛት።
ዙሪያቸውን እንደ እንቦቀቅላ ህፃን ድክ ድክ የሚሉት
እርግቦች አንዳች ነገር እንደመጣባቸው ሁሉ ድንገት ግር ብለው ወደ
ሃይቁ አቅጣጫ በረሩ።
አኜስ የአሌክስን እጆች ወርውራ እርግቦችን
ተመለከታቸው።
እጥፍ ብለው እንደገና ሽቅብ ጎነው በረሩ: አሌክስ ፊቷን ወደ እሱ አዙሮ
“ሰርቶ መበልፀግ ስመኘው የኖርሁትን እድል በማግኘቴ
ረክቻለሁ። ፍቅራችን ከብልፅግና ማግስት.. ጆሮዋ ደነቆረ: ከዚያ በኋላ የሚለውን አልሰማችውም።
ፍቅር ከብልፅግና
ማግስት…" አባባሉ በአእምሮዋ አስተጋባ:
ዛሬን አበላሽቶ ነገን ማስዋብ ፍቅርን ገፍትሮ ጥቅምን ማቀፍ
ተምታታባት እሪ ብለሽ ጩሂ አሰኛት… መጮህ ግን ተሳናት::ለመጮሀም ኃይል ያስፈልጋል።
አሌክስን ጠላችው 1
ገፋችው... ከዚያ እርግቦቹ ወደ ሄዱበት አቅጣጫ በረረች “አዕዋፍ ለካ ወደው ከምድር ርቀው አይበሩም ብላ በአየር ላይ ለመብረር ወደ ሰማዬ ሰማያት ለመጎን ሞከረች ትናንሽ ፍጡራን የፈፀሙትን ግን መፈፀም ተሳናት።
ይህ ከሆነና ከአሌክስ በተለየች በአምስት ዓመቷ “አሽቀንጥሬ ጣልሁት ያለችው የከንፈር ወዳጅዋ አንደገና ራባት። ፍቅሩ አገርሽቶ ጤና አሳጣት ስለዚህ ፓርቶሪኮን ለመጎብኘት በሚል ሽፋን ወደ ሳንጁአን ሄደች።
ሳን ጁአን እንደደረስችም አሌክስ በሰጣት የእርሻ ጣቢያ ማዕከል አዳራሻ ሄዳ አሌክስን እንዲያገናኝዋት ጠየቀች። በእርግጥ
👍28
በእእምሮዋ ብዙ ነገር ተፈራረቀባት። ፍቅሩ ጭካኔው. ግዴለሽነቱ
ወንዳወንድነቱ ስሜቷን አምታቱባት ናፍቀዋለች፤ ግን ፍቅሯን አንኮሻክሻ ሰባብሮታል: ለብዙ ጊዜ ልትረሳው ሞክራለች ድንገት ግን ፍቅሩ ያቃዣታል
የስራ ባልደረቦቹ ማንነቷንና ያላቸውን ግንኙነት ከጠየቋት በኋላ እንድትጠነክር በመምከር “ አሌክስ ለሽርሽር ይዟት በወጣው ጀልባ የአደጋው መንስኤ ባይታወቅም አደጋ ደርሶበት በህክምና
ሊፈወስ ባለመቻሉ አረፈ..." ብለው አረዷት።
ከዚያ ማንን ለማምለጥ መሆኑ ግራ በሚያጋባ ሁኔታ በመጣችበት አቅጣጫ ሮጠች:: ለዚያች ውብ ከማዘን በስተቀር
የተከተላት ግን አልነበረም: ሃዘኗን አንጂ የአጣችው ፍቅር ምን ያህል ባዶ ብቸኛ አድርጎ ድቅድቅ ጨለማ ውስጥ እንደዶላት የተረዳ
የለም: ይህ ስሜት አይተው የሚረዱት አይደለም ከርቀት ሲያዩት ገለባ ነው ቀላል።
እንደ ቋጥኝ ድንጋይ እየተንከባለለ መጥቶ አከርካሪው የደቀቀበት ያፈቀረውን ያጣ በሽተኛ
ግን ስቃዩን ህመሙን
ስለሚያውቀው ያዝን ይሆናል። አኜስ ግን በጊዜው አዛኝ አላገችም:
ስለዚህ ከመከራዋ
እንደምታመልጥ ሁሉ
ሮጠች።ከግቢው እንደወጣች ቀጥታ ይዟት ወደ መጣው ታክሲ
ውስጥ ገባች። ገራገሩ ሾፌር፦
“ሲኞሪታ! የተከበሩ እመቤቴ! ወዴት ይዥዎት ልሂድ? ሲላት እንደ በሰለ ቲማቲም ፊቷ ቀልቶ አስተዋለ።
“ክብር አልፈልግም
ገባህ? አኜስ ብለህ ጥራኝ: ከአሁኑ ሰዓት ጀምሮ ወደ ፈለከው ይዘኸኝ ልትሄድ ትችላለህ: እኔ ደግሞ
የጠየቅኸኝን ሒሳብህን እh
እከፍልሃለሁ" አለችው።
ግር ያለው የታhሲ ሾፌር እንደገና ዘወር ብሎ አያት::
ከእሱ አንፃር ወጣት ናት። ከአቅሟ በላይ የሆነ መረበሽ ግን ያትነከነክናታል። ችግሯን ባይረዳውም አዘነላት:: ሰዎች ሲረበሹ ፀሐይ ወጥታ የምትገባ አይመስላቸውም። ይች ዓለም ለዝንተ ዓለም
በጨለማ ተውጣ የምትቀር ስለሚመስላቸው የሚሰሩትን አያውቁም'
ብሉ አሰበና! “እባክሽን
ለመረጋጋት ሞክሪንና
ከዚያ መሄድ ወደምትፈልጊው
አደርስሻለሁ" አላት ፍፁም በኃዘኔታ ስሜት:
“ማረፍ እፈልጋለሁ መሸሽ እፈልጋለሁ... መኪናህን
አስነሳና ይዘኸኝ ሂድ" አለችው።
“ወዴት ልውስድሽ?" ብሎ እንዳዘዘችው የመኪናውን ሞተር ሲያስነሳ።
“ወደምትኖርበት ወደምትፈልገው ይዘኸኝ ሂድ" አለችው።
ጤና ያጣች መሰለው፡ ይበልጥም አዘነላት። ወደ ሆስፒታል ሊወስዳት ቢጠይቃት ጆሮ ግንዱ ላይ ጮኸችበት።
እኔ ያጣሁ የነጣሁ አፍሪካዊ ነኝ፡ ከኔ ጋር ያሰብሽው ፍፁም እብድነት ነው" ሲላት ደግማ አንቧረቀችበትና፡
ጤነኛ ነኝ! ጤነኛ ነኝ! ስቃዩ ሰዎች በሽታ ከሚሉት
ዝርዝር ውስጥ የለም... አሁን ወደምትወስደኝ ውሰደኝ አለችው:
ሾፌሩ ጉዞውን ጀመረና ወደ ጥቁሮች ሰፈር ይዟት ገባ።
ከዛ... የኮንችት እናት ከሪና ተፀነሰች የከሪና መወለድ ደግሞ አኜስና አፍሪካዊው ሉካዬ ስፔን ውስጥ አብረው እንዲኖሩ ምክንያት
ሆናችው..
💫ይቀጥላል💫
ወንዳወንድነቱ ስሜቷን አምታቱባት ናፍቀዋለች፤ ግን ፍቅሯን አንኮሻክሻ ሰባብሮታል: ለብዙ ጊዜ ልትረሳው ሞክራለች ድንገት ግን ፍቅሩ ያቃዣታል
የስራ ባልደረቦቹ ማንነቷንና ያላቸውን ግንኙነት ከጠየቋት በኋላ እንድትጠነክር በመምከር “ አሌክስ ለሽርሽር ይዟት በወጣው ጀልባ የአደጋው መንስኤ ባይታወቅም አደጋ ደርሶበት በህክምና
ሊፈወስ ባለመቻሉ አረፈ..." ብለው አረዷት።
ከዚያ ማንን ለማምለጥ መሆኑ ግራ በሚያጋባ ሁኔታ በመጣችበት አቅጣጫ ሮጠች:: ለዚያች ውብ ከማዘን በስተቀር
የተከተላት ግን አልነበረም: ሃዘኗን አንጂ የአጣችው ፍቅር ምን ያህል ባዶ ብቸኛ አድርጎ ድቅድቅ ጨለማ ውስጥ እንደዶላት የተረዳ
የለም: ይህ ስሜት አይተው የሚረዱት አይደለም ከርቀት ሲያዩት ገለባ ነው ቀላል።
እንደ ቋጥኝ ድንጋይ እየተንከባለለ መጥቶ አከርካሪው የደቀቀበት ያፈቀረውን ያጣ በሽተኛ
ግን ስቃዩን ህመሙን
ስለሚያውቀው ያዝን ይሆናል። አኜስ ግን በጊዜው አዛኝ አላገችም:
ስለዚህ ከመከራዋ
እንደምታመልጥ ሁሉ
ሮጠች።ከግቢው እንደወጣች ቀጥታ ይዟት ወደ መጣው ታክሲ
ውስጥ ገባች። ገራገሩ ሾፌር፦
“ሲኞሪታ! የተከበሩ እመቤቴ! ወዴት ይዥዎት ልሂድ? ሲላት እንደ በሰለ ቲማቲም ፊቷ ቀልቶ አስተዋለ።
“ክብር አልፈልግም
ገባህ? አኜስ ብለህ ጥራኝ: ከአሁኑ ሰዓት ጀምሮ ወደ ፈለከው ይዘኸኝ ልትሄድ ትችላለህ: እኔ ደግሞ
የጠየቅኸኝን ሒሳብህን እh
እከፍልሃለሁ" አለችው።
ግር ያለው የታhሲ ሾፌር እንደገና ዘወር ብሎ አያት::
ከእሱ አንፃር ወጣት ናት። ከአቅሟ በላይ የሆነ መረበሽ ግን ያትነከነክናታል። ችግሯን ባይረዳውም አዘነላት:: ሰዎች ሲረበሹ ፀሐይ ወጥታ የምትገባ አይመስላቸውም። ይች ዓለም ለዝንተ ዓለም
በጨለማ ተውጣ የምትቀር ስለሚመስላቸው የሚሰሩትን አያውቁም'
ብሉ አሰበና! “እባክሽን
ለመረጋጋት ሞክሪንና
ከዚያ መሄድ ወደምትፈልጊው
አደርስሻለሁ" አላት ፍፁም በኃዘኔታ ስሜት:
“ማረፍ እፈልጋለሁ መሸሽ እፈልጋለሁ... መኪናህን
አስነሳና ይዘኸኝ ሂድ" አለችው።
“ወዴት ልውስድሽ?" ብሎ እንዳዘዘችው የመኪናውን ሞተር ሲያስነሳ።
“ወደምትኖርበት ወደምትፈልገው ይዘኸኝ ሂድ" አለችው።
ጤና ያጣች መሰለው፡ ይበልጥም አዘነላት። ወደ ሆስፒታል ሊወስዳት ቢጠይቃት ጆሮ ግንዱ ላይ ጮኸችበት።
እኔ ያጣሁ የነጣሁ አፍሪካዊ ነኝ፡ ከኔ ጋር ያሰብሽው ፍፁም እብድነት ነው" ሲላት ደግማ አንቧረቀችበትና፡
ጤነኛ ነኝ! ጤነኛ ነኝ! ስቃዩ ሰዎች በሽታ ከሚሉት
ዝርዝር ውስጥ የለም... አሁን ወደምትወስደኝ ውሰደኝ አለችው:
ሾፌሩ ጉዞውን ጀመረና ወደ ጥቁሮች ሰፈር ይዟት ገባ።
ከዛ... የኮንችት እናት ከሪና ተፀነሰች የከሪና መወለድ ደግሞ አኜስና አፍሪካዊው ሉካዬ ስፔን ውስጥ አብረው እንዲኖሩ ምክንያት
ሆናችው..
💫ይቀጥላል💫
👍32
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ
ጆሮዎቹ ላይ ሉቲ አንጠልጥሏል ጥቁር ቆዳው ላይ አልፎ
አልፎ ቡግር መሣይ ነጠብጣቦች ይታያሉ: አገጩ ጠበብ ብሎ
ቁጥርጥር ያሉት ፂሙ ፀጉሮቹ አልፎ አልፎ ጉች ጉች ብለዋል።
አይኖቹ ቦዘዝ ብለው የጭካኔ የእንቢተኝነት... እይታ ይታይባቸዋል። ሶራ የኮንችትን አያት ፎቶ ግራፍ ሲመለከት ቆይቶ ሲጋራውን አቀጣጥሎ ወደ መቀመጫው ተመለሰ።
ኮንችት ከወደ ውስጥ በሩን ከፍታ ብቅ ስትል ቤቱ በምግብ ሽታ ታፈነ። ከዚያ የተጣጠፉ የጠረዼዛ ልብሶችን እያነጣጠፈች
ሰሃን ማንኪያ ሹካ እየደረደረች።
“ወንድ አያቴ ሴት አያቴን በፍቅር ልቧን ጠምዝዞ የጣላት እንዴት እንደሆነ ልንገርህ" አለችው ሙሉ ለሙሉ በፈገግታ ወደ
እሱ ዞራ።
የጡቶችዋ ጎንና ጎኖች ታዩት፡ ጫፋቸው ደግሞ ጋዋኗን ወጠር አድርጎት ተመለከተ። ሰርጓዳ እምብርቷን አይቶ ዝቅ ሲል
ደግሞ ነጭ ፓንቷን አየ የታባክ ተመለስ እንደተባለ ሁሉ እንደመርበትበት ብሎ
“ምን አልሽኝ?" አላት:
“ሴት አያቴ በወንዱ አያቴ ፍቅር እንዴት እንደወደቀች
ልንገርህ"
“እሽ በምናቸው ነው?''
በዝምታው ነው” አለችው።
“ዝምታው!” ተደንቆ አያት:
አዎ!
ዝምታው” አለችውና ቀኝ እግሯን አንዱ ወንበር
ላይ አስቀምጣ ሙሉ ለሙሉ ለስላሳ ጭኗን እያሳየችው ስታየው፡-
“አልገባኝም” አላት ግራ ትከሻውን ሰብቆ። እሷም ጠረጴዛው ላይ አስፈላጊ የሆኑትን ነገሮች ማዘጋጀቷን እያረጋገጠች፡-
“አዝናለሁ! እይታ እንጂ ማብራሪያ ሊገልፀው አይችልም:: ዝምታ ግን የሴት አያቴን የፍቅር ልብ ማሸነፉ እውነት ነው"
ብላው ወደ ጓዳ ገባች::
ሶራ ምክንያቷን ለመስማት ጆሮዎቹን እንዳቆመ ጠበቃት።የበሰሉና የቆርቆሮ ምግቦችን እየደረደረች በመካከሉ ቀና ብላ አይታው፡-
“እዚህ ገባ ስትል መታጠቢያና መፀዳጃ ታገኛለህ። በኔ በኩል
አስፈላጊውን ሁሉ እዘጋጅቼ የጨረስሁ ይመስለኛል" ብላ አንድ የቲማቲም ቁራጭ በሹካዋ አንስታ ዋጠች።
ሶራ ወደ ጠቆመችው ክፍል ገብቶ ተጣጥቦ ወጣ፡
የስፔን ባህላዊ ምግብ ጃፓሾ ፒላ... ክሪም በእንቁላል ከወይን ጋር ጠረዼዛው ላይ ተደርድሯል።
“ቦና ፔቲ" አለችው ኮንችት እንብላ ለማለት በፈረንሳይኛ።
"ሳቅ ብሎ “ሜርሲ” አላት: ፈረንሳይኛ, እንግሊዘኛ መቻሏ አስተሳሰቧ በአመለካከቷ አድማስ መጨመር የሚኖረው ጠቀሜታ ታየው:: የአስተሳሰብ ብስለት ከሚያመጡ ምክንያቶች አንዱ ብዙ ቋንቋ ተናጋሪ መሆንና ሌላውን ለማንበብ መቻል እንደሆነ ያውቃል።
ይህን እያሰበ የሚፈልገውን ከአነሳ በኋላ አንገቱን አቀርቅሮ ሲበላ ቆየና ቀና ሲል እሷ ሰሃን ላይ ምንም ምግብ የለም።
“አትበይም?'' አላት ወደ ምግቡ በቢላዋው እየጠቆመ፡
አይኖችቿን በልጠጥ አድርጋ አመሠግናለሁ: ደስ ሲለኝ ብዙ አልበላም" አለችው።
“ለቅርፅሽ እንዳይሆን ፈገግ ብሉ ጠቃት:
“ለዚያ ቢሆን ከልቤ ነው የምጨነቀው:"
“ለምን?”
“ቅጥነት ውበት መሆኑን ገና በመዋለ ህናት እያለሁ
ስለማውቅ" ፈገግ አለች
ጭኖቹ ላይ ያስቀመጠውን “ናፕኪን' አንስቶ አፉን እያበሰ፤
“አዎ! ሴት ልጅ ቀጠን ስትል ውበቷ ይፈካል" ሲል
አቋረጠችውና፡-
“ወንድም ቢሆን ዘርጠጥ ከሚል ከወደ ሆዱ ሰብሰብ ሲልና ትከሻው ሲሰፋ ለሴት ልጅ የደረት ላይ ዋና አመች ይሆናል" ብላ ፈገግ ስትል ሶራ ደነገጠ። ከደረቱ ይልቅ ሆዱ አብጧል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ቢሆን
ኖር እንዴት አማረብህ?”
የሚያሰኘው ውፍረቱ ያኔ አሳፈረው፡
ሆዱ ወደ ውስጥ ሊሸልገው ሞከረ:: ህሊናው ግን “ዘገየህ”ብሎ አሾፈበት: ቅርዑን ጠላው።
መብላቱንም አቆመ።
“ምነው?” አለችው ኮንችት በመገረም እያየችው።
ምኑ?" አላት ስሜቱን ለመደበቅ እየጣረ።
“ሀሳብ የያዘህ ትመስላለህ?"
ደህና ነኝ" አለና ዘና ብሎ ቁጭ አለ።
ኮንችት ከተቀመጠችበት ተነስታ ሶፋው ላይ እግሮችዋን አጣጥፋ ቁጭ ስትል ተነስቶ ወደ መታጠቢያ ክፍሉ ገባ።
ውሃውን ከፍቶ ጎረድ ያለ አፍንጫውን ቦግ ቦግ ያሉ
አይኖቹንን ጠይም ፊቱን ተመልክቶ ጎንበስ ብሎ ሆዱን አየው:በሁለት እጁ ሆዱን ከፍሉ የተከመረውን ትርፍ በጥላቻ ተመልከቶ
"ቆርጦ መጣል ነበር ብሎ ተመኘና ፊቱን በውሃ አበስ አበስ አድርጎ ወጣ።
“ሆዴን እንዴት ጠላሁት መሰለሽ አላት ወደ መቀመጫው እየሄደ።
“ዘገየህ” አለችው ዘና ብላ፡
“ለምኑ? አላት ፈገግ ብሎ።
“ግልፅነት ይጎድልሃል አንደ የሚያስጨንቅህ ነገር
እንደነበር ስለተረዳሁ ስጠይቅህ ደበቅኸኝ፡ አሁን ግን ሳልጠይቅህ
ነገርኸኝ... ደካማነት ነው" አለችውና፡-
“ሆድህን ግን ለምን ጠላኸው?''
“...ለዋና ስለማይመች" አላት።
“ባለህ እንኳ የምትኮራ መሆን አለብህ። ለውበትና ለጤንነት መስተካከል ሽንቃጣነት ምርጫህ ካልሆነ ለሴት ብለህ አካላዊ ለውጥ መፈለግ የለብህም: ሴት ልጅ በባህር ውስጥ ጠልቃ የፍቅር ሉል
ማውጣት በአስተሳሰብ በስለት ወይንም በሌሎች የራሷ ምክንያት
የምትፈልገውን ለመምረጥ እምትቸግር አይደለችም ግን አንድ ነገር አትጣ” ስትለው
“ምን?” አላት ፈጠን ብሎ።
"ለሴት ልጅ ቅርፅ ብቻ ወሳኝ አይደለም፡ ህሊናዊ ይዘትንም የመፈተሽ ተፈጥሮአዊ ፀጋ አላት። ብቻ የሚፈቀር ነገር አትጣ።
ይዘቱም ቅርፁም ባዶ ከሆነባት እንደ ሎጥ ሚስት ገትራህ ፊቷን ሳታዞር ትሄዳለች አለችና ራሷን ሶፋው ላይ አስተኝታ ሳቀች::
ክሊሊሊ..ሊ እያለ የሚያስተጋባው ሳቋ በውስጡ አንዳች ስሜት
ፈጠረበት:: ሳቋ የተለመደ አይነት አይደለም። ግን የሚያውቀው
እንዲያውም ሲያዳምጣቸው ስሜቱን ከሚያዝናኑት ሙዚቃዎች እንደ አንዱ ቆጠረው:
“እኔ እንደምገምተው" ብላ እግሮችዋን ፈርከክ አድርጋ
የእግሮችዋን ጣቶች በእጆችዋ ጣቶች እየደባበሰች ሳለች ነጩን ፓንት እንደገና አየው።
“በአዳምና ሔዋን ዘመን ፍቅርን የጀመረችና የሰጠች ሔዋን ናት: አዳም በእግዚአብሔር ስም ዳቦዋን ቆረሰው፤እና አብረው ተካፍለው በሉት፤ አጣጣሙት:: ከዚያን ጊዜ ወዲሆ ሴት ልጅ
በወንድ አካል ጠልቃ የፍቅር ሉል ለማውጣት የምትፈልገው አንድ
ነገር ብቻ ነው” አለችው።
“ምን?” ሲላት ኮንችት ፈገግ ብላ፦
ጊዜ አነስተኛ ጊዜ" አለችው።
“እንዳባባልሽ እንግዲህ ፍቅርን የፈጠረች ሴት ናት ማለት ነው ሲል።
“የፈጠረች የሚለውን የጀመረች ካልነው እውነተኛው መላምት ይህ ይመስለኛል" አለችው
"ወንዶችስ?”
ወንዶችማ ሲበዛ ስሜታዊ ናችሁ: ወደ ስር ለመጥለቅና የፍቅር ሉል ለማግኘት የዋና ስልት የላችሁም:: ላይ ለላይ ያዝ ለቀቅ ማረጉን ትመርጣላችሁ: ይህ ደግሞ የተፈጥሮ ችግራችሁ ነው:
ጥልቁን የፍቅር ሉል የምትፈልጉት በሆዳችሁ እንጂ በልባችሁ
አይደለም
ሶራ ፀጥ ብሎ ማሰቡን መረጠ፡
'ውብ... ለስላሳ... አስተሳስብ በሳል. ሞልቃቃ...' እያለ ስለሷ
ሲያስብ በተከፈተው ጭኗ እንደገና አየው። ነጭ ፓንቷን…
💫ይቀጥላል💫
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታሰ
ጆሮዎቹ ላይ ሉቲ አንጠልጥሏል ጥቁር ቆዳው ላይ አልፎ
አልፎ ቡግር መሣይ ነጠብጣቦች ይታያሉ: አገጩ ጠበብ ብሎ
ቁጥርጥር ያሉት ፂሙ ፀጉሮቹ አልፎ አልፎ ጉች ጉች ብለዋል።
አይኖቹ ቦዘዝ ብለው የጭካኔ የእንቢተኝነት... እይታ ይታይባቸዋል። ሶራ የኮንችትን አያት ፎቶ ግራፍ ሲመለከት ቆይቶ ሲጋራውን አቀጣጥሎ ወደ መቀመጫው ተመለሰ።
ኮንችት ከወደ ውስጥ በሩን ከፍታ ብቅ ስትል ቤቱ በምግብ ሽታ ታፈነ። ከዚያ የተጣጠፉ የጠረዼዛ ልብሶችን እያነጣጠፈች
ሰሃን ማንኪያ ሹካ እየደረደረች።
“ወንድ አያቴ ሴት አያቴን በፍቅር ልቧን ጠምዝዞ የጣላት እንዴት እንደሆነ ልንገርህ" አለችው ሙሉ ለሙሉ በፈገግታ ወደ
እሱ ዞራ።
የጡቶችዋ ጎንና ጎኖች ታዩት፡ ጫፋቸው ደግሞ ጋዋኗን ወጠር አድርጎት ተመለከተ። ሰርጓዳ እምብርቷን አይቶ ዝቅ ሲል
ደግሞ ነጭ ፓንቷን አየ የታባክ ተመለስ እንደተባለ ሁሉ እንደመርበትበት ብሎ
“ምን አልሽኝ?" አላት:
“ሴት አያቴ በወንዱ አያቴ ፍቅር እንዴት እንደወደቀች
ልንገርህ"
“እሽ በምናቸው ነው?''
በዝምታው ነው” አለችው።
“ዝምታው!” ተደንቆ አያት:
አዎ!
ዝምታው” አለችውና ቀኝ እግሯን አንዱ ወንበር
ላይ አስቀምጣ ሙሉ ለሙሉ ለስላሳ ጭኗን እያሳየችው ስታየው፡-
“አልገባኝም” አላት ግራ ትከሻውን ሰብቆ። እሷም ጠረጴዛው ላይ አስፈላጊ የሆኑትን ነገሮች ማዘጋጀቷን እያረጋገጠች፡-
“አዝናለሁ! እይታ እንጂ ማብራሪያ ሊገልፀው አይችልም:: ዝምታ ግን የሴት አያቴን የፍቅር ልብ ማሸነፉ እውነት ነው"
ብላው ወደ ጓዳ ገባች::
ሶራ ምክንያቷን ለመስማት ጆሮዎቹን እንዳቆመ ጠበቃት።የበሰሉና የቆርቆሮ ምግቦችን እየደረደረች በመካከሉ ቀና ብላ አይታው፡-
“እዚህ ገባ ስትል መታጠቢያና መፀዳጃ ታገኛለህ። በኔ በኩል
አስፈላጊውን ሁሉ እዘጋጅቼ የጨረስሁ ይመስለኛል" ብላ አንድ የቲማቲም ቁራጭ በሹካዋ አንስታ ዋጠች።
ሶራ ወደ ጠቆመችው ክፍል ገብቶ ተጣጥቦ ወጣ፡
የስፔን ባህላዊ ምግብ ጃፓሾ ፒላ... ክሪም በእንቁላል ከወይን ጋር ጠረዼዛው ላይ ተደርድሯል።
“ቦና ፔቲ" አለችው ኮንችት እንብላ ለማለት በፈረንሳይኛ።
"ሳቅ ብሎ “ሜርሲ” አላት: ፈረንሳይኛ, እንግሊዘኛ መቻሏ አስተሳሰቧ በአመለካከቷ አድማስ መጨመር የሚኖረው ጠቀሜታ ታየው:: የአስተሳሰብ ብስለት ከሚያመጡ ምክንያቶች አንዱ ብዙ ቋንቋ ተናጋሪ መሆንና ሌላውን ለማንበብ መቻል እንደሆነ ያውቃል።
ይህን እያሰበ የሚፈልገውን ከአነሳ በኋላ አንገቱን አቀርቅሮ ሲበላ ቆየና ቀና ሲል እሷ ሰሃን ላይ ምንም ምግብ የለም።
“አትበይም?'' አላት ወደ ምግቡ በቢላዋው እየጠቆመ፡
አይኖችቿን በልጠጥ አድርጋ አመሠግናለሁ: ደስ ሲለኝ ብዙ አልበላም" አለችው።
“ለቅርፅሽ እንዳይሆን ፈገግ ብሉ ጠቃት:
“ለዚያ ቢሆን ከልቤ ነው የምጨነቀው:"
“ለምን?”
“ቅጥነት ውበት መሆኑን ገና በመዋለ ህናት እያለሁ
ስለማውቅ" ፈገግ አለች
ጭኖቹ ላይ ያስቀመጠውን “ናፕኪን' አንስቶ አፉን እያበሰ፤
“አዎ! ሴት ልጅ ቀጠን ስትል ውበቷ ይፈካል" ሲል
አቋረጠችውና፡-
“ወንድም ቢሆን ዘርጠጥ ከሚል ከወደ ሆዱ ሰብሰብ ሲልና ትከሻው ሲሰፋ ለሴት ልጅ የደረት ላይ ዋና አመች ይሆናል" ብላ ፈገግ ስትል ሶራ ደነገጠ። ከደረቱ ይልቅ ሆዱ አብጧል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ቢሆን
ኖር እንዴት አማረብህ?”
የሚያሰኘው ውፍረቱ ያኔ አሳፈረው፡
ሆዱ ወደ ውስጥ ሊሸልገው ሞከረ:: ህሊናው ግን “ዘገየህ”ብሎ አሾፈበት: ቅርዑን ጠላው።
መብላቱንም አቆመ።
“ምነው?” አለችው ኮንችት በመገረም እያየችው።
ምኑ?" አላት ስሜቱን ለመደበቅ እየጣረ።
“ሀሳብ የያዘህ ትመስላለህ?"
ደህና ነኝ" አለና ዘና ብሎ ቁጭ አለ።
ኮንችት ከተቀመጠችበት ተነስታ ሶፋው ላይ እግሮችዋን አጣጥፋ ቁጭ ስትል ተነስቶ ወደ መታጠቢያ ክፍሉ ገባ።
ውሃውን ከፍቶ ጎረድ ያለ አፍንጫውን ቦግ ቦግ ያሉ
አይኖቹንን ጠይም ፊቱን ተመልክቶ ጎንበስ ብሎ ሆዱን አየው:በሁለት እጁ ሆዱን ከፍሉ የተከመረውን ትርፍ በጥላቻ ተመልከቶ
"ቆርጦ መጣል ነበር ብሎ ተመኘና ፊቱን በውሃ አበስ አበስ አድርጎ ወጣ።
“ሆዴን እንዴት ጠላሁት መሰለሽ አላት ወደ መቀመጫው እየሄደ።
“ዘገየህ” አለችው ዘና ብላ፡
“ለምኑ? አላት ፈገግ ብሎ።
“ግልፅነት ይጎድልሃል አንደ የሚያስጨንቅህ ነገር
እንደነበር ስለተረዳሁ ስጠይቅህ ደበቅኸኝ፡ አሁን ግን ሳልጠይቅህ
ነገርኸኝ... ደካማነት ነው" አለችውና፡-
“ሆድህን ግን ለምን ጠላኸው?''
“...ለዋና ስለማይመች" አላት።
“ባለህ እንኳ የምትኮራ መሆን አለብህ። ለውበትና ለጤንነት መስተካከል ሽንቃጣነት ምርጫህ ካልሆነ ለሴት ብለህ አካላዊ ለውጥ መፈለግ የለብህም: ሴት ልጅ በባህር ውስጥ ጠልቃ የፍቅር ሉል
ማውጣት በአስተሳሰብ በስለት ወይንም በሌሎች የራሷ ምክንያት
የምትፈልገውን ለመምረጥ እምትቸግር አይደለችም ግን አንድ ነገር አትጣ” ስትለው
“ምን?” አላት ፈጠን ብሎ።
"ለሴት ልጅ ቅርፅ ብቻ ወሳኝ አይደለም፡ ህሊናዊ ይዘትንም የመፈተሽ ተፈጥሮአዊ ፀጋ አላት። ብቻ የሚፈቀር ነገር አትጣ።
ይዘቱም ቅርፁም ባዶ ከሆነባት እንደ ሎጥ ሚስት ገትራህ ፊቷን ሳታዞር ትሄዳለች አለችና ራሷን ሶፋው ላይ አስተኝታ ሳቀች::
ክሊሊሊ..ሊ እያለ የሚያስተጋባው ሳቋ በውስጡ አንዳች ስሜት
ፈጠረበት:: ሳቋ የተለመደ አይነት አይደለም። ግን የሚያውቀው
እንዲያውም ሲያዳምጣቸው ስሜቱን ከሚያዝናኑት ሙዚቃዎች እንደ አንዱ ቆጠረው:
“እኔ እንደምገምተው" ብላ እግሮችዋን ፈርከክ አድርጋ
የእግሮችዋን ጣቶች በእጆችዋ ጣቶች እየደባበሰች ሳለች ነጩን ፓንት እንደገና አየው።
“በአዳምና ሔዋን ዘመን ፍቅርን የጀመረችና የሰጠች ሔዋን ናት: አዳም በእግዚአብሔር ስም ዳቦዋን ቆረሰው፤እና አብረው ተካፍለው በሉት፤ አጣጣሙት:: ከዚያን ጊዜ ወዲሆ ሴት ልጅ
በወንድ አካል ጠልቃ የፍቅር ሉል ለማውጣት የምትፈልገው አንድ
ነገር ብቻ ነው” አለችው።
“ምን?” ሲላት ኮንችት ፈገግ ብላ፦
ጊዜ አነስተኛ ጊዜ" አለችው።
“እንዳባባልሽ እንግዲህ ፍቅርን የፈጠረች ሴት ናት ማለት ነው ሲል።
“የፈጠረች የሚለውን የጀመረች ካልነው እውነተኛው መላምት ይህ ይመስለኛል" አለችው
"ወንዶችስ?”
ወንዶችማ ሲበዛ ስሜታዊ ናችሁ: ወደ ስር ለመጥለቅና የፍቅር ሉል ለማግኘት የዋና ስልት የላችሁም:: ላይ ለላይ ያዝ ለቀቅ ማረጉን ትመርጣላችሁ: ይህ ደግሞ የተፈጥሮ ችግራችሁ ነው:
ጥልቁን የፍቅር ሉል የምትፈልጉት በሆዳችሁ እንጂ በልባችሁ
አይደለም
ሶራ ፀጥ ብሎ ማሰቡን መረጠ፡
'ውብ... ለስላሳ... አስተሳስብ በሳል. ሞልቃቃ...' እያለ ስለሷ
ሲያስብ በተከፈተው ጭኗ እንደገና አየው። ነጭ ፓንቷን…
💫ይቀጥላል💫
👍46❤1🔥1
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሮፕላን እያጉረመረመ ከለንደኑ ሒትሮ አውሮፕላን ማረፊያ ተነስቶ የለንደኑን ዳመና በአፍንጫው
እየበረቃቀሰ አቅጣጫውን ካስተካከለ በኋላ ካርለት ከሎና ጎይቲ እንደ ሌሎቹ መንገደኞች ሣቅ ጨዋታ አላበዙም።
ካርለትና ጎይቲ እየቆዩ ጫን ጫን ይተነፍሳሉ። ሶስቱም
የተቀመጡት በአሮፕላኑ መካከል ባሉት መቀመጫዎች ጎን ለጎን
ሲሆን ከፊት ለፊታቸውና ከኋላቸው ነጮችአሉ በስተቀኝ በኩል
አንድ ኢትዮጵያዊና አንድ ነጭ፤ በስተግራ በኩል ደግሞ የንጉሥ
ኃይለስላሴን ምስል ደረታቸው ላይ ያንጠለጠሉ ፀጉራቸውን እንደ ባህታዊ ጎንጉነው የኢትዮጵያ ባንዲራ የጠመጠሙ ጃማይካውያን
ተቀምጠዋል።
ካርለት በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚታተመውን “ሰላምታ" መጽሔት እያነበበች ሳለች።
“ይቅርታ” የሚል ድምፅ ሰምታ ቀና ስትል የአሮፕላኑ
አስተናጋጅ ፈገግ ብላ የምግብ ማስቀመጫውን እንዲዘረጉ ጠይቃ
ለሶስቱም የሚሆነውን ምግብ በፊታቸው አስቀመጠች።
በአጭር ጊዜ ውስጥ በኤሮፕላኑ ውስጥ ያለው ተሳፋሪ መመገብ ጀመረ: ጎይቲ ልትበላ አልፈለገችም: ካርለት ግን፡-
“ጎይቲ እባክሽ ትንሽ ለመብላት ሞክሪ?" አለቻት፡
“ካርለት እህል መች ራበኝ። ይልቅንስ አንች ብይ" አለቻት ፈርጠም ብላ ጎይቲ።
ባይሆን ይሄ ደረቅ ስለሆነ ብስኩቱን ብይ እስፕራይቱንም
ጠጪ" ስትላት።
“ይእ! አቤት! የምግባችሁ ስሙ ብዛቱ። አፍ ላይ
ይጣፍጥና ውስጥ ሲገባ እንደ ነፍሰ ጡር ማቅለሽለሽ። አሁንስ ወደ
አገሬ እሄድሁ ነው:: ለኔ ያደግሁበት ኩርኩፋ ትኩስ ወተቴ ይሻለኛል፡" ጎይቲ ኮስተር አለች።
ከሎና ካርለት ተያዩ: ጎይቲ አንዴ ከወሰነች ውሳኔዋን
እንደማታጥፍ ስላወቁ የየበኩላቸውን መመገብ ጀመሩ::
ጎይቲ ወዲያ ወዲህ ሄድ መለስ የሚሉትን እያየች ቆየችና፡-
“ፈረንጅና ህፃን ልጅ አንድ ነው፡ አንድ ጊዜ እስኪጠግብ አይበላ! አሁንም አሁንም መለካከፍ! ሁሉን መላስ ብቻ አንዴ
ጥሩ አርጎ አይጎርስ አይ ደንብ እቴ: ይእ! - ደግሞ የልብሳቸወ ብዛት:: ልብስን ቢያበዙት ትርፍ የለው: ከብት ቢገዙት ይራባል
በረት ይሞላል፤ ተዚያ ወተቱ ስጋው ይጠቅማል። ለዘመድ ወገን ቢሸልሙት ደስ ይላል።
“እነሱ ቤታቸውን ኮሮጆአቸውን የሞላው የሚያልቅ ቅራቅንቦ ብቻ! እና እኒህ ከህፃን በምን ይሻላሉ። እንደ ቀበሮ
የሚፈልጉትን እየተሯሯጡ ሲያነፈነፉ ይውሉና በዚያ ተግቶ በሚውለው ዋሻቸው ገብተው ማድፈጥ: እርስ በርስ አይዋደዱ አንዱ ሌላው ዘንድ አይደርስ ሲጫወቱ ለከት የላቸው:: ጆሮ እሚያደነቁር ነገር ይከፍቱና ዛር እንደያዘው ሰው አንዱ ከመሬት
መፈጥፈጥ ሌላው እንደ ጠገበ እንቦሳ መዝለል... ወንድና ሴቱ ደግሞ አይታወቅ ሁለቱም እቤት ውስጥ ተከተው አንድ አልጋ
ላይ ወጥተው መተኛት። ሴት ወንድን እንደህፃን ልጅ አቅፋ ተኝታ ሲያንኮራፋ ማየት።
“ደሞ የዚህ የኔው ጉድ የከሎ ይባስ እንጂ! ወዷቸው ሊሞት! ሳያርፍ ደሞ መኖርስ እዚህ ነበር' ይበለኝ፡ መጨከኑ
እንደ ዶሮ ሲጠጡ ማንጋጠጥ ሲበሉ አንገት መድፋት ከዚያ መሮጥ እንደ እብድ እየተገፋፉ መክላፍለፍ ተመልሶ ዋሻን ዘግቶ መቀመጥ ይህ የቀበሮ ኑሮ ምን ይወደዳል? ይእ! እነ አያ ደልቲ! ሐመሮች እዚህ ውስጥ መኖሬን ብነግራቸው እውን ሰው ያረጉኛል።ዳሩ እኒስ ምን ጥሩ አለው ብዬ አወራቸዋለሁ። ብቻ እንድረስ!"ጎይቲ ስለ ነጮች አኗኗር ማሰቧም ዘገነናት።
ጎይቲ አይኖችዋ ቡዝዝ ብለው ቢከፈቱም አያዩም: እሷ የምታየው የሐመር ተራራን ሜዳን... የጀግኖችን ቁንጮ ደልቲ ገልዲን ነው::
ቱር እያሉ የሚበሩ አዕዋፍ በነፋስ ጎንበስ ቀና የሚሉት
እዕዋት... ሳራቸውን የሚያመነዥኩ ከብቶች በጎችና ፍየሎች በጨረቃ ብርሃን ተቃቅፈው የሚጨፍሩት ልጃገረዶችና ጎረምሶች በአይነ ህሊናዋ ይመጡባታል፧ ይታይዋታል::
ደልቲን ለዳንስ ስትጋብዘው አየሩን እየቀዘፈ የወተት አረፋ የመሰለ ጥርሱን በጨረቃዋ ብርሃን እያብለጨለጨ ሲመጣ ከወገቧ እየረገረገች ጡቶችዋን እያስነጠረች ስልቱ ባልተዘበራረቀ እንቅስቃሴ መሬት እስኪጨንቃት እየረገጠ ሲጠጋትና ስትሾር... እንደ ብረት የጠነከሩት እጆቹ ትከሻዋን ሲደገፉ እንደ ባልጩት የሚለሰልሰው
ጭኑ ወደ ጭኗ ሲዘልቅ የብልቷ በር ደጋግሞ ሲንኳኳ... ከዚያ ወደ
ተፈጥሮ መኝታ ቤት ወደ ጫካው ሲገቡ በሩ ተከፍቶ ጋ ተደርጎ ሲቀረቀር የፍቅር ማራቸውን ሲላላሱ እንዳይሰላቹ ተሰነባብተው
እሷ ወደ ጎጆዋ እሱ ወደ ማማው ሲያመሩ ታያት።
ይህን ጊዜ ጎይቲ
ካርለት! ምነው ይኸ ነገር ቆመ፤ ምነው የሰው ጭንቀት ቢገባው ፤ምናለ! ከሐመር ቀዬ ቶሎ በሮ ቢያደርሰኝ!... አለቻት
መሳሳቋን ሳትደብቅ።
“እንደ ወፍ እየበረርን ነው'ኮ ጎይቲ! አይዞሽ ወደ ናፈቅሽው ቶሎ ትደርሻለሽ: ከሎን አታየውም? አለቻት እንድትረጋጋ በማሰብ
“ይእ! እሱማ ለማዳ ነው። ታቦቱ ደንብ የወረሰው የለም ለኔ የጨነቀኝ ለሱ ደስታ ፈጥሮለታል። ብቻ ተይኝ! እንዲያው እሚሰሙሽ ከሆነ ይኸ ነገሩ በቋራጭ በአቋራጭ አድርጎ ከሐመር
hእባቴ ተራራ ከቡስካ እንዲጥለኝ ንገሪው:: ከዚያስ ወዲያ ችግር
ቀናም ብዬ ሳላየው እየቦረቅሁ ተቀየዬ
ከዘመዶቼ ከጀግናዬ ጋር እገናኛለሁ፡ እና! እስቲ ንገሪቸው? አለች ጎይቲ፡
ካርለት ሳቅ ብላ፦
“ኤሮፕላኑ የራሱ የተወሰነ ፍጥነት ኦለው..." ስትል ጎይቲ አቋረጣት።
"አቤት! የደንባችሁ ብዛቱ። አቤት ስትፈራሩ… በይ ተይው እኔስ እንግዲህ ለአንድ ጊዜ እችለዋለሁ። መጥኔ ለናንተ! አለቻትና
ወደ ህልሟ ገባች። ከሎ ከጃማይካዎች ጋር ይጫወታል ይከራhራል...ይሳሳቃል።
የጎይቲ አስተያየት
ካርለት እንደ ሌላው ጊዜ ሁሉ አስገረማት። የጎይቲን ገሀዳዊ ህይወት አይታዋለች: ሐመሮች
በጥቁር ቆዳ የተሸፈነ አልማዝ ጥቅማ ጥቅም ያልበከለው ንፁህ ህሊና ያልተበከለ ባህል ካለ ዘመናዊ ህግና ፖሊሲ ተስማምተው
የሚኖሩ ተፈጥሮን የማይቃረኑ ህዝቦች መሆናቸውን አብራቸው
ኖራ አይታለች።
ሐመር ውስጥ ስሜት በህሊና እንጂ ሰዎች ባወጡት ህግ
አልተለጎመም: እውነት ራቁቷን ናት! እነሱም ራቁታቸውን ናቸው!
ተፈጥሮም አልተበከለችም! መሬት የፈለገችውን እፅዋት ታበቅላለች!የተጠጓትን አውሬዎች ደስ ብሉአቸው እንዲኖሩ ታረጋለች
የተፈጥሮ አበባ አካባቢውን እንዳስዋበው ነው። ሰማዩ ግን በአይሮፕላን ጢስ እየቆሸሸ መኪናው አራዊትን እያስበረገገ ነው።ስልጣኔ የተፈጥሮ ሚዛንን ለማዛባት ኬላውን ለመጣስ እየጣረ ነው ያኔ በራስ መተማመን በራሱ ይቆማል! ህክምና አልባው የመምስል
በሽታ ይጠናወታል! ማንነት ይጠፋል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የመስኮቱ መጋረጃ እንደተዘጋ ነው: የመኝታ ክፍሉ ግን በማለዳ ፀሐይ ብርሃን ደምቋል። ካርለት ተንጠራርታ አይኖችዋን
ስትከፍት ነጭ ቀለም የተቀባውን የመኝታ ክፍል ከጣራው እስከ ወለሉ የሚደርሰውን ሰፊ ቁምሳጥን ሰፊውን አልጋ.. ቃኝታ ዘወር ስትል ከስቲቭ ጋር ተያዩ::
ተንጠራርታ ወደሱ ጠጋ አለችና በፀጉር ከተሸፈነው ደረቱ ላይ ተለጥፋ አቀፈችው። እሱም ያቀፈበትን ክንዱን ሳብ ሳብ አድርጎ በግራ እጁ ፀጉሯን ዳበሰላት።
መቀሽቀሻ ስዓቷ ዲሪሪን… ዲሪሪን.ዲሪሪን' ስትል ስቲቭ ቀና ብሎ ድምፅ ሲያሰማት ፀጥ አለች እነሱም ሙቀታቸውን
እየተጋሩ ተቃቅፈው ፀጥ አሉ።
መቀሽቀሻ ሰዓቷ ከአምስት ደቂቃ በኋላ ደግማ ዲሪሪን…..ዲሪሪን...' ስትል ካርለት የስቲቭን ከንፈር ሳም አድርጋ ቢጃማዋን
ሳትለብስ እርቃኗን መታጠቢያ ክፍል ገባች።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሮፕላን እያጉረመረመ ከለንደኑ ሒትሮ አውሮፕላን ማረፊያ ተነስቶ የለንደኑን ዳመና በአፍንጫው
እየበረቃቀሰ አቅጣጫውን ካስተካከለ በኋላ ካርለት ከሎና ጎይቲ እንደ ሌሎቹ መንገደኞች ሣቅ ጨዋታ አላበዙም።
ካርለትና ጎይቲ እየቆዩ ጫን ጫን ይተነፍሳሉ። ሶስቱም
የተቀመጡት በአሮፕላኑ መካከል ባሉት መቀመጫዎች ጎን ለጎን
ሲሆን ከፊት ለፊታቸውና ከኋላቸው ነጮችአሉ በስተቀኝ በኩል
አንድ ኢትዮጵያዊና አንድ ነጭ፤ በስተግራ በኩል ደግሞ የንጉሥ
ኃይለስላሴን ምስል ደረታቸው ላይ ያንጠለጠሉ ፀጉራቸውን እንደ ባህታዊ ጎንጉነው የኢትዮጵያ ባንዲራ የጠመጠሙ ጃማይካውያን
ተቀምጠዋል።
ካርለት በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚታተመውን “ሰላምታ" መጽሔት እያነበበች ሳለች።
“ይቅርታ” የሚል ድምፅ ሰምታ ቀና ስትል የአሮፕላኑ
አስተናጋጅ ፈገግ ብላ የምግብ ማስቀመጫውን እንዲዘረጉ ጠይቃ
ለሶስቱም የሚሆነውን ምግብ በፊታቸው አስቀመጠች።
በአጭር ጊዜ ውስጥ በኤሮፕላኑ ውስጥ ያለው ተሳፋሪ መመገብ ጀመረ: ጎይቲ ልትበላ አልፈለገችም: ካርለት ግን፡-
“ጎይቲ እባክሽ ትንሽ ለመብላት ሞክሪ?" አለቻት፡
“ካርለት እህል መች ራበኝ። ይልቅንስ አንች ብይ" አለቻት ፈርጠም ብላ ጎይቲ።
ባይሆን ይሄ ደረቅ ስለሆነ ብስኩቱን ብይ እስፕራይቱንም
ጠጪ" ስትላት።
“ይእ! አቤት! የምግባችሁ ስሙ ብዛቱ። አፍ ላይ
ይጣፍጥና ውስጥ ሲገባ እንደ ነፍሰ ጡር ማቅለሽለሽ። አሁንስ ወደ
አገሬ እሄድሁ ነው:: ለኔ ያደግሁበት ኩርኩፋ ትኩስ ወተቴ ይሻለኛል፡" ጎይቲ ኮስተር አለች።
ከሎና ካርለት ተያዩ: ጎይቲ አንዴ ከወሰነች ውሳኔዋን
እንደማታጥፍ ስላወቁ የየበኩላቸውን መመገብ ጀመሩ::
ጎይቲ ወዲያ ወዲህ ሄድ መለስ የሚሉትን እያየች ቆየችና፡-
“ፈረንጅና ህፃን ልጅ አንድ ነው፡ አንድ ጊዜ እስኪጠግብ አይበላ! አሁንም አሁንም መለካከፍ! ሁሉን መላስ ብቻ አንዴ
ጥሩ አርጎ አይጎርስ አይ ደንብ እቴ: ይእ! - ደግሞ የልብሳቸወ ብዛት:: ልብስን ቢያበዙት ትርፍ የለው: ከብት ቢገዙት ይራባል
በረት ይሞላል፤ ተዚያ ወተቱ ስጋው ይጠቅማል። ለዘመድ ወገን ቢሸልሙት ደስ ይላል።
“እነሱ ቤታቸውን ኮሮጆአቸውን የሞላው የሚያልቅ ቅራቅንቦ ብቻ! እና እኒህ ከህፃን በምን ይሻላሉ። እንደ ቀበሮ
የሚፈልጉትን እየተሯሯጡ ሲያነፈነፉ ይውሉና በዚያ ተግቶ በሚውለው ዋሻቸው ገብተው ማድፈጥ: እርስ በርስ አይዋደዱ አንዱ ሌላው ዘንድ አይደርስ ሲጫወቱ ለከት የላቸው:: ጆሮ እሚያደነቁር ነገር ይከፍቱና ዛር እንደያዘው ሰው አንዱ ከመሬት
መፈጥፈጥ ሌላው እንደ ጠገበ እንቦሳ መዝለል... ወንድና ሴቱ ደግሞ አይታወቅ ሁለቱም እቤት ውስጥ ተከተው አንድ አልጋ
ላይ ወጥተው መተኛት። ሴት ወንድን እንደህፃን ልጅ አቅፋ ተኝታ ሲያንኮራፋ ማየት።
“ደሞ የዚህ የኔው ጉድ የከሎ ይባስ እንጂ! ወዷቸው ሊሞት! ሳያርፍ ደሞ መኖርስ እዚህ ነበር' ይበለኝ፡ መጨከኑ
እንደ ዶሮ ሲጠጡ ማንጋጠጥ ሲበሉ አንገት መድፋት ከዚያ መሮጥ እንደ እብድ እየተገፋፉ መክላፍለፍ ተመልሶ ዋሻን ዘግቶ መቀመጥ ይህ የቀበሮ ኑሮ ምን ይወደዳል? ይእ! እነ አያ ደልቲ! ሐመሮች እዚህ ውስጥ መኖሬን ብነግራቸው እውን ሰው ያረጉኛል።ዳሩ እኒስ ምን ጥሩ አለው ብዬ አወራቸዋለሁ። ብቻ እንድረስ!"ጎይቲ ስለ ነጮች አኗኗር ማሰቧም ዘገነናት።
ጎይቲ አይኖችዋ ቡዝዝ ብለው ቢከፈቱም አያዩም: እሷ የምታየው የሐመር ተራራን ሜዳን... የጀግኖችን ቁንጮ ደልቲ ገልዲን ነው::
ቱር እያሉ የሚበሩ አዕዋፍ በነፋስ ጎንበስ ቀና የሚሉት
እዕዋት... ሳራቸውን የሚያመነዥኩ ከብቶች በጎችና ፍየሎች በጨረቃ ብርሃን ተቃቅፈው የሚጨፍሩት ልጃገረዶችና ጎረምሶች በአይነ ህሊናዋ ይመጡባታል፧ ይታይዋታል::
ደልቲን ለዳንስ ስትጋብዘው አየሩን እየቀዘፈ የወተት አረፋ የመሰለ ጥርሱን በጨረቃዋ ብርሃን እያብለጨለጨ ሲመጣ ከወገቧ እየረገረገች ጡቶችዋን እያስነጠረች ስልቱ ባልተዘበራረቀ እንቅስቃሴ መሬት እስኪጨንቃት እየረገጠ ሲጠጋትና ስትሾር... እንደ ብረት የጠነከሩት እጆቹ ትከሻዋን ሲደገፉ እንደ ባልጩት የሚለሰልሰው
ጭኑ ወደ ጭኗ ሲዘልቅ የብልቷ በር ደጋግሞ ሲንኳኳ... ከዚያ ወደ
ተፈጥሮ መኝታ ቤት ወደ ጫካው ሲገቡ በሩ ተከፍቶ ጋ ተደርጎ ሲቀረቀር የፍቅር ማራቸውን ሲላላሱ እንዳይሰላቹ ተሰነባብተው
እሷ ወደ ጎጆዋ እሱ ወደ ማማው ሲያመሩ ታያት።
ይህን ጊዜ ጎይቲ
ካርለት! ምነው ይኸ ነገር ቆመ፤ ምነው የሰው ጭንቀት ቢገባው ፤ምናለ! ከሐመር ቀዬ ቶሎ በሮ ቢያደርሰኝ!... አለቻት
መሳሳቋን ሳትደብቅ።
“እንደ ወፍ እየበረርን ነው'ኮ ጎይቲ! አይዞሽ ወደ ናፈቅሽው ቶሎ ትደርሻለሽ: ከሎን አታየውም? አለቻት እንድትረጋጋ በማሰብ
“ይእ! እሱማ ለማዳ ነው። ታቦቱ ደንብ የወረሰው የለም ለኔ የጨነቀኝ ለሱ ደስታ ፈጥሮለታል። ብቻ ተይኝ! እንዲያው እሚሰሙሽ ከሆነ ይኸ ነገሩ በቋራጭ በአቋራጭ አድርጎ ከሐመር
hእባቴ ተራራ ከቡስካ እንዲጥለኝ ንገሪው:: ከዚያስ ወዲያ ችግር
ቀናም ብዬ ሳላየው እየቦረቅሁ ተቀየዬ
ከዘመዶቼ ከጀግናዬ ጋር እገናኛለሁ፡ እና! እስቲ ንገሪቸው? አለች ጎይቲ፡
ካርለት ሳቅ ብላ፦
“ኤሮፕላኑ የራሱ የተወሰነ ፍጥነት ኦለው..." ስትል ጎይቲ አቋረጣት።
"አቤት! የደንባችሁ ብዛቱ። አቤት ስትፈራሩ… በይ ተይው እኔስ እንግዲህ ለአንድ ጊዜ እችለዋለሁ። መጥኔ ለናንተ! አለቻትና
ወደ ህልሟ ገባች። ከሎ ከጃማይካዎች ጋር ይጫወታል ይከራhራል...ይሳሳቃል።
የጎይቲ አስተያየት
ካርለት እንደ ሌላው ጊዜ ሁሉ አስገረማት። የጎይቲን ገሀዳዊ ህይወት አይታዋለች: ሐመሮች
በጥቁር ቆዳ የተሸፈነ አልማዝ ጥቅማ ጥቅም ያልበከለው ንፁህ ህሊና ያልተበከለ ባህል ካለ ዘመናዊ ህግና ፖሊሲ ተስማምተው
የሚኖሩ ተፈጥሮን የማይቃረኑ ህዝቦች መሆናቸውን አብራቸው
ኖራ አይታለች።
ሐመር ውስጥ ስሜት በህሊና እንጂ ሰዎች ባወጡት ህግ
አልተለጎመም: እውነት ራቁቷን ናት! እነሱም ራቁታቸውን ናቸው!
ተፈጥሮም አልተበከለችም! መሬት የፈለገችውን እፅዋት ታበቅላለች!የተጠጓትን አውሬዎች ደስ ብሉአቸው እንዲኖሩ ታረጋለች
የተፈጥሮ አበባ አካባቢውን እንዳስዋበው ነው። ሰማዩ ግን በአይሮፕላን ጢስ እየቆሸሸ መኪናው አራዊትን እያስበረገገ ነው።ስልጣኔ የተፈጥሮ ሚዛንን ለማዛባት ኬላውን ለመጣስ እየጣረ ነው ያኔ በራስ መተማመን በራሱ ይቆማል! ህክምና አልባው የመምስል
በሽታ ይጠናወታል! ማንነት ይጠፋል።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የመስኮቱ መጋረጃ እንደተዘጋ ነው: የመኝታ ክፍሉ ግን በማለዳ ፀሐይ ብርሃን ደምቋል። ካርለት ተንጠራርታ አይኖችዋን
ስትከፍት ነጭ ቀለም የተቀባውን የመኝታ ክፍል ከጣራው እስከ ወለሉ የሚደርሰውን ሰፊ ቁምሳጥን ሰፊውን አልጋ.. ቃኝታ ዘወር ስትል ከስቲቭ ጋር ተያዩ::
ተንጠራርታ ወደሱ ጠጋ አለችና በፀጉር ከተሸፈነው ደረቱ ላይ ተለጥፋ አቀፈችው። እሱም ያቀፈበትን ክንዱን ሳብ ሳብ አድርጎ በግራ እጁ ፀጉሯን ዳበሰላት።
መቀሽቀሻ ስዓቷ ዲሪሪን… ዲሪሪን.ዲሪሪን' ስትል ስቲቭ ቀና ብሎ ድምፅ ሲያሰማት ፀጥ አለች እነሱም ሙቀታቸውን
እየተጋሩ ተቃቅፈው ፀጥ አሉ።
መቀሽቀሻ ሰዓቷ ከአምስት ደቂቃ በኋላ ደግማ ዲሪሪን…..ዲሪሪን...' ስትል ካርለት የስቲቭን ከንፈር ሳም አድርጋ ቢጃማዋን
ሳትለብስ እርቃኗን መታጠቢያ ክፍል ገባች።
👍31👏1
ከተደረደረው የገላ መታጠቢያ ሻምፖ “ፋ” የሚለውን አንስታ ከታጠበች በኋላ በፎጣ ፀጉሯን ጠቅልላ ጥርሶችዋን
በመቦረሽ ልብሷን ለማምጣት ከመታጠቢያ ክፍሉ ወጣች።
ስቲቭ እንደተኛ ነው: ሁሌም መኝታውን ለመልቀቅ
ለረጅም ደቂቃዎች አልጋው ውስጥ አመድ ላይ እንደሚንከባለል አህያ ግራና ቀኝ መዟዟር አለባት: ካርለት ደግሞ ጠዋት መነሳትና የአዕዋፍን ዝማሬ እያዳመጠች ስራ እንኳን ባይኖራት መንጎዳጎዱን
ትመርጣለች። የዛን ቀን ግን ብርቱ ጉዳይ ነበራት።
“ስቲቭ?" አለችው ወደ አልጋው ጠርዝ ጠጋ ብላ:
“እህ!” አላት በድካም መንፈስ። ጎንበስ ብላ ከንፈሩን ስማው ቀና ስትል መዓዛውን የያዘውን አየር ባፍንጫው ሳበና “ዋው..” ብሎ ፈገግ አለ።
“ስቲቭ ስማ! ከሎና ጎይቲ ዛሬ ወደ ሐመር መሄድ
አለባቸው:: ጎይቲ አዲስ በበባ ውስጥ ማደር መዋል አትፈልግም::ናፍቆቷ ከልክ አልፏል። ፍላጎቷን ለማሳካት ደግሞ መሄድ አለባት::
ከሎ ግን ጥቂት ቀናት አዲስ አበባ ለመቆየት ፈልጎ ነበር። እሱ አዚህ
እንዳይቆይ ደግሞ እኔም የግድ ወደ ዩንቨርሊቲ መሄድና ከአንዳንድ
ሰዎች ጋር መገናኘት ምግቦችን... መገዛዛት አለብኝ።
“በተጨማሪም አያቷ ኢትዮጵያዊ የሆነች ስፔናዊት የአያቷን ትውልድ ቦታና ዘመዶችዋን ማየት እንደምትፈልግ እረፍት ስፔን
በቆየሁበት ጊዜ አጫውታኝ ኢትዮጵያ ብትመጣ በመፈለጉ ላይ ልተባበራት እንደምችል ቃል ገብቼላታለሁ: ስለዚህ ከከሎ ይልቅ የኔ እዚህ መቆየት የግድ ነው" ስትለው
“ጥሩ ነው!” አላት ስቲቭ። ቀጥላ ግን
“የመኪናው ባትሪ የት ነው? አለችው።
“ትናንት መልሰው እንዲያሰሩት ስለነገርኳቸው አስረውታል።ዘይት በመቀየር የሚፈትሽውን ሁሉ በመፈተሽ መኪናውን
ሞክረውት ለጉዞ ዝግጁ መሆኑን የኛ መካኒኮች አረጋግጠውልኛል!
ቁልፉ እሳሎን ተንጠልጥሏል"
“አመሰግናለሁ ስቲቭ"
“ለምኑ?” አለ ፈገግ ብሉ።
“ላስቆጠርከው መልካም ሥራ ሁሉ” አለችና እንደገና ስማው ወጣች።
💫ይቀጥላል💫
በመቦረሽ ልብሷን ለማምጣት ከመታጠቢያ ክፍሉ ወጣች።
ስቲቭ እንደተኛ ነው: ሁሌም መኝታውን ለመልቀቅ
ለረጅም ደቂቃዎች አልጋው ውስጥ አመድ ላይ እንደሚንከባለል አህያ ግራና ቀኝ መዟዟር አለባት: ካርለት ደግሞ ጠዋት መነሳትና የአዕዋፍን ዝማሬ እያዳመጠች ስራ እንኳን ባይኖራት መንጎዳጎዱን
ትመርጣለች። የዛን ቀን ግን ብርቱ ጉዳይ ነበራት።
“ስቲቭ?" አለችው ወደ አልጋው ጠርዝ ጠጋ ብላ:
“እህ!” አላት በድካም መንፈስ። ጎንበስ ብላ ከንፈሩን ስማው ቀና ስትል መዓዛውን የያዘውን አየር ባፍንጫው ሳበና “ዋው..” ብሎ ፈገግ አለ።
“ስቲቭ ስማ! ከሎና ጎይቲ ዛሬ ወደ ሐመር መሄድ
አለባቸው:: ጎይቲ አዲስ በበባ ውስጥ ማደር መዋል አትፈልግም::ናፍቆቷ ከልክ አልፏል። ፍላጎቷን ለማሳካት ደግሞ መሄድ አለባት::
ከሎ ግን ጥቂት ቀናት አዲስ አበባ ለመቆየት ፈልጎ ነበር። እሱ አዚህ
እንዳይቆይ ደግሞ እኔም የግድ ወደ ዩንቨርሊቲ መሄድና ከአንዳንድ
ሰዎች ጋር መገናኘት ምግቦችን... መገዛዛት አለብኝ።
“በተጨማሪም አያቷ ኢትዮጵያዊ የሆነች ስፔናዊት የአያቷን ትውልድ ቦታና ዘመዶችዋን ማየት እንደምትፈልግ እረፍት ስፔን
በቆየሁበት ጊዜ አጫውታኝ ኢትዮጵያ ብትመጣ በመፈለጉ ላይ ልተባበራት እንደምችል ቃል ገብቼላታለሁ: ስለዚህ ከከሎ ይልቅ የኔ እዚህ መቆየት የግድ ነው" ስትለው
“ጥሩ ነው!” አላት ስቲቭ። ቀጥላ ግን
“የመኪናው ባትሪ የት ነው? አለችው።
“ትናንት መልሰው እንዲያሰሩት ስለነገርኳቸው አስረውታል።ዘይት በመቀየር የሚፈትሽውን ሁሉ በመፈተሽ መኪናውን
ሞክረውት ለጉዞ ዝግጁ መሆኑን የኛ መካኒኮች አረጋግጠውልኛል!
ቁልፉ እሳሎን ተንጠልጥሏል"
“አመሰግናለሁ ስቲቭ"
“ለምኑ?” አለ ፈገግ ብሉ።
“ላስቆጠርከው መልካም ሥራ ሁሉ” አለችና እንደገና ስማው ወጣች።
💫ይቀጥላል💫
👍22
‹የተሰባበሩ ነፍሶች››
ምዕራፍ16
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
/
የዳይመንድ ኢንተርናሺናል ሆስፒታል ዋና መግቢያ በራፍ በአድማ በታኝ ፖሊሶች ታጥሯል…በሆስፒታሉ ቀደም ብለው በውስጡ ተኝተው ከሚታከሙት ታካሚዎች ውጭ አዲስ ታካሚ መቀበል ካቆመ ሁለት ቀን አልፎታል፡፡ ወደሆስፒታሉ የሚያስገባው የአስፓልት መንገድና በአከባቢው የሚገኘው አደባባይ ጠቅላላ በሰላማዊ ሰልፍ አድራጊዎች ተጨናንቆል፡፡በሰላማዊ ሰልፉ ላይ የሚሰሙ መፈክሮች ውስጥ ጥቂቱ
‹‹ፍትህ ለዶ/ር ሰጵራ››
‹‹የዚህ ወንጀል ማስተር ማይንድ ፕሮፌሰሩ ነው››
‹‹ፖሊሶች ስራችሁን ስሩ››
‹‹ፈትህ ኩላሊታችውና ልባቸው ለተዘረፉ ዜጎች ››
‹‹ከዚህ ጀርባ ያላችሁ ባለስልጣን ወየሁላችሁ››
‹‹ፕሮፌሰሩ አጭበርባሪ ነው››
ይሄ ሁሉ ግርግራና ሰላማዊ ሰልፈ ሊወጣ የቻለው አብዬት በተሰባበሩ ነፍሶች የፌስብክ ገፅ ዶክተሯ መታፈኗንና ያፈኗት የፕሮፌሰሩ ሰዎች ከሆኑ ወንጀላቸውን እንዳታጋልጥበቸው እስከአሁን ገድለዋት ሊሆን እንደሚችል ጥርጣሬ እንዳለው መረጃውን ከለቀቀ ብኃላ ነው፡፡
ከዛ ደግሞ አንድ የግል የቴሌቬዝን ጣቢያ(እርግጥ ለጣቢያው ጋዘጠኛ አብዬት ከፍሎታል)ጎንደር ድረስ ሄዶ ታግተው የነበሩ እናቷንና እህቷን ኤንተርቨው አድርጎ አየር ላይ ካዋለው ብኃላ የዶ/ሯ ጉዳይ ሀገራዊ ችግር ሆነ..ትላልቅ ባለስልጣኖች ጉዳዩ ምንድነው ?ብለው መጠየቅ ሲጀምሩ ጉዳዩ ውስጥ የነበሩበት ባለስልጣኖች ደግሞ የሚይዙት የሚጨብጡት ጠፍቶቸው መተረማመስ ጀመሩ፡፡
..
ግፊት እነ ጫና ሲበዛበት ፖሊስ መግለጫ ሰጠ
ዶ/ር ሰጳራን ያገቷትን ሰዎችን በማደን ላይ አንደሆነና በአሁኑ ጊዜ ፕሮፌሰሩና ሙሉ የተባለው የፕሮፌሰሩ አጋር መሰወራቸውንና ከሀገር ለመውጣት እቅድ እንደነበራቸው መረጃው ስለደረሰው በየትኛውም መንገድ ከሀገር እንዳይወጡ ከፍተኛ ክትትል እየተደረገባቸው እንደሆ ገልፀው ከህብረተሰብም ውስጥ ፕሮፌሰሩንና አጋራቸውን ያሉበን የሚያውቅ ካለ በመጠቆም እንዲተባበር አሳወቁ
//
ዶ/ር ሰጳራና ካሳ በምቹ የሆቴል ክፍል ውስጥ ከታገቱ ሶስት ቀን ሆኗቸዋል፡፡በዚህ ሶስት ቀን ውስጥ ማንም ሰው እኔ ነኝ ያገትኮችሁ ብሎ ያናገራቸው የለም፡፡ግን በራፍቸው ላይ በተጠንቅ 24 ሰዓት የሚጠበብቆቸው ጠባቂዎቻቸው የፈለጉትን ነገሮች ሁሉ ከጥቂት የተከለከሉ እንደሞባይል ያሉ እቃዎች በስተቀር በፍጥነትና ያለማቅማማት ያቀርቡላቸዋል፡፡፡ዶ/ር ምንም እንኳን በመጀመሪያው ቀናቶች የቤተሰቦቾ ነገሮች በጣም እያሳሳባት ስለነበረ እሷ እርፍት አጠጥታ ጠባቂዎቹን በጭቅጭቅ እርፍት ነስታቸው የነበር ቢሆንም ከትናንትና ጀምሮ ግን ቤተሰቦቾ መለቃቸውን እንደውም እናቷንና እህቷን ስለደረሰባቸው ጉዳይ ሲያስረዱ ቀጥታ በቴሊቪዝን ካየች ቡኃላ በጣም ተረጋግታለች፡:፡ካሳ ደግሞ ከመጀመሪያ ቀን አንስቶ እጅግ ደስተኛ ሆኗል፡እንደውም ከከተማ ወጣ ብሎ ሳባና ቢች አካባቢ ባለ ቤርጎ ዘና እያለ ነው ሚመስለው፡፡
ካሳ ከፊት ለፊቷ ተቀምጦ አይን አይኗን እያያት‹‹ዶ/ር እነዚህ ሰዎች ምን ያህል የተባረኩ ናቸው?››አላት
‹‹የእኔ ጅል …የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ እኮ መገደልህ አይቀርም››
‹‹እንዴ ልገደላ …ሞት እኮ መቼም አይቀርልንም…..ግን ይሄው ካንቺ ጋር የሶስት ቀን ገነታዊ የሆነ የጫጉላ ጊዜ እንዳሳልፍ እረድተውኛል...ለእኔ በጣም ባለውለታዬ ናቸው…››
‹‹የጫጉላ ጊዜ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ትርጉሙንም አታውቅም እንዴ?››
‹‹ቀላል ነው ከሚወዶት ሴት ጋር ለብቻ ተገልሎ የብቻ የሆነ ደስታ ጊዜ ማሳለፍ ማለት ነው››
‹‹በቃ››
‹‹አዎ በቃ… ከዛ በላይ ምን አለ?››
‹‹አለ ጂሉ....ለብቻቸው ተገልላው፤ የብቻ ጊዜ ማሳለፋቸው ብቻ ሳይሆን እንዴት እየሳለፉ ነው የሚለውም ወሳኝ ጉዳይ ነው..የጫጉላ ጊዜ ብዙ መሳሳም አለ…መተቃቀፍ አለ..መተሻሸት አለ ፤መዋሰብ አለ..ልጅ መስራት አለ››ከገባው ብላ ዘረዘረቸለት
‹‹በቃ?›አላት በተራው
‹‹ምነው? ልጨምር››
እነዚህን የዘረዘርሻቸው እኮ የፍቅር ማስዋቢያዎች ናቸው...እኔ ደግሞ ፍቅርን በሌሎች ነገሮች መኳኳል አልፈልግም..
እና አሁን እሺ ብዬህ ብንጋባም ምንም አንፈፅምም ማለት ነው?››
‹‹እኔ ብዙም አልፈልግም..ግን አንቺ ምትፈልጊ ከሆነ ችግር የለውም…ወሲብም ሆነ መሳሳሙን ላንቺ ስል አደረገዋለሁ››አላት፤ከእሱ የጠበቀችውን መልስ ነበር ያገኘችው፡፡
‹‹ስለዚህ ይሄንን የጫጉል ጊዜ ላመቻቹልህ ተወዳጆቹ አጋቾችህ ህይወትህን ብትሰጣቸውም ቅር አይልህም ማለት ነው?›አለቺው፡፡
‹‹በትክክል…በተለይ ቆይታችንን ለአንድ ሳማንት ቢያራዝሙልን››
ኣንድ ሰምንት››ዘገነናት…ከዛሬ ነገ ሊገድሉኝ ነው እያሉ የገዛ መሞቻ ጊዜን እየጠበቁ ለአንድ ሳምንት መጠበቅ ከባድ ነው፡፡
‹‹የሆንክ ዊርድ ነገር እኮ ነህ…..ከአንድ ሰው ጋር ዝም ብሎ ለሳምንት ተፋጦ መቀመጠ አያስጨንቅህም?››
‹‹አዎ በጣም ደባሪ ነገር ነው...ከአንድ ሰው ጋር በአንድ ክፍል ውስጥ ለአንድ ቀን እንኳን ተዘግቶብኝ ቢሆን በንዴት እራሴን ላጠፋ ሁሉ እችል ነበር..ችግሩ አንቺ ሌላ ሰው አይደለቺም…..አንቺ ማለት እራሴው ነሽ…ከራሴው ጋ ደግሞ ለዘላለም ብቀመጥ ችግር የለውም››
‹‹አይ አንተ… ጅል አፍቃሪ ነህ እኮ….››አለችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ጉንጩን ሳመችው…..ዞር ብላ ወደ መቀመጫዋ ልትመለስ ስትል አይኞቾ ቴሊቭዝኑ ላይ አረፉ… ሪሞቱን አነሳችን ድምፅን ጨምራበት አጠገቧ ያለው ወንበር ላይ ቁጭ ብላ ማየት ጀመረች…ጉዳዩ ሙሉ በሙሉ ስለእነሱ የሚያወራ ስለሆነ ነው ቀልቧን የሳባት፡፡ የሆስፒታላቸው ዋና ባለሼር የሆኑት ሼክ ጠሀ ፊታቸው ለተደረደሩት በቁጥር አምስት ለሚሆኑ ጋዜጠኞች ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጡ ነው፡፡
ክብርን የአትዬጵያ ህዝቦች በሆስፒታላችን ላይ በተከሰተው ጊዜያው ቀውስ በጣም እናዝናለን፡፡ግን እመኑኝ በአጭር ቀናት ውስጥ ከፖሊሶች ጋር በመተባበር በሆስፒታላችን ስም ጀርባ ተሸጉጠው ለአመታት ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩትን ሰዎች በማደን በህግ ተይዘው ፍትህ እንዲሰጣቸው ማድረግ ብቻ ሳይሆን ካለጥፋታቸው በወንጀለኞቹ አሻጥር ሲሳደዱ የነበሩትን ባለደረቦቻችንን ደግሞ በሰላም ወደቤታው እንዲመለሱ ማድረግ ዋና ስራችን ይሆናል፡፡
አንድ ጋዜጠና ማይኩን ወደራሱ አስጠጋና ጥያቄውን ማቅማረብ ጀመረ‹‹ፓሊስ በሰጠው መግለጫ ከሆስፒታሉ ዋና ዋና ባለአክሲዬኖች መካከል ሁለቱ ማለቴ ፕሮፌሰሩና አቶ ሙሉ የተባሉት ግለሰቦች ተሰውረዋል…ታግተዋል የሚሉ ጭምጭምታዎችም አሉ…በዚህ ጉዳይ ላይ ምን አስተያየት አሎት?›
መመለስ ጀመሩ‹‹ፕሮፌሰሩ እና አቶ ሙሉ የሆስፒታሉ ባለአክሲዎኖች ብቻ ሳይሆኑ ሆስፒታሉንም ዋናና ምክትል ሆነው ለአመታት ሲያስተዳድሩ የነበሩ ሰዎች ናቸው.፡፡በሆስፒታሉ የምትከወን እያንዳንዶ ጥቃቅን ነገር ሳትቀር ከእነዚህ ሰዎች እውቅን ውጭ አትከወንም….እና እንደእኔ ግመት እነዚህን ሰዎች ታግተው ሳይሆን ተሸሽገው ወይንም ከሀገር ለመውጣት ሙከራ ላይ ያሉ ይመስለኛል…..ዶ/ር ሰጵራንም አግተዋት ከሆነ በጣም ደጎች ከሆኑ(ፕሮፌሰሩ እጮኛው እንደሆነች ከግምት በማስገባት)ይዘዋት ሊወጡ ይችላሉ…..ካልሆነም አላህ ቸሩን ያሰማን ብቻ……..ግን ፕሮፌሰሩና ግብረ አበሩ ሰሞኑን ከየወዳጆቻቸው ዶላር እየጠየቁ እንደነበር መስማት ችለናል……እቤታቸውም በፖሊስ ሲፈተሸ..ዋና ዋና እቃቸውን በሻንጣ ሞልተው ከቤት እንደወጡ ማወቅ ተችሏል፡፡የሚታገት ሰው ደግሞ እንደዚህ አይደለም›
ምዕራፍ16
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
/
የዳይመንድ ኢንተርናሺናል ሆስፒታል ዋና መግቢያ በራፍ በአድማ በታኝ ፖሊሶች ታጥሯል…በሆስፒታሉ ቀደም ብለው በውስጡ ተኝተው ከሚታከሙት ታካሚዎች ውጭ አዲስ ታካሚ መቀበል ካቆመ ሁለት ቀን አልፎታል፡፡ ወደሆስፒታሉ የሚያስገባው የአስፓልት መንገድና በአከባቢው የሚገኘው አደባባይ ጠቅላላ በሰላማዊ ሰልፍ አድራጊዎች ተጨናንቆል፡፡በሰላማዊ ሰልፉ ላይ የሚሰሙ መፈክሮች ውስጥ ጥቂቱ
‹‹ፍትህ ለዶ/ር ሰጵራ››
‹‹የዚህ ወንጀል ማስተር ማይንድ ፕሮፌሰሩ ነው››
‹‹ፖሊሶች ስራችሁን ስሩ››
‹‹ፈትህ ኩላሊታችውና ልባቸው ለተዘረፉ ዜጎች ››
‹‹ከዚህ ጀርባ ያላችሁ ባለስልጣን ወየሁላችሁ››
‹‹ፕሮፌሰሩ አጭበርባሪ ነው››
ይሄ ሁሉ ግርግራና ሰላማዊ ሰልፈ ሊወጣ የቻለው አብዬት በተሰባበሩ ነፍሶች የፌስብክ ገፅ ዶክተሯ መታፈኗንና ያፈኗት የፕሮፌሰሩ ሰዎች ከሆኑ ወንጀላቸውን እንዳታጋልጥበቸው እስከአሁን ገድለዋት ሊሆን እንደሚችል ጥርጣሬ እንዳለው መረጃውን ከለቀቀ ብኃላ ነው፡፡
ከዛ ደግሞ አንድ የግል የቴሌቬዝን ጣቢያ(እርግጥ ለጣቢያው ጋዘጠኛ አብዬት ከፍሎታል)ጎንደር ድረስ ሄዶ ታግተው የነበሩ እናቷንና እህቷን ኤንተርቨው አድርጎ አየር ላይ ካዋለው ብኃላ የዶ/ሯ ጉዳይ ሀገራዊ ችግር ሆነ..ትላልቅ ባለስልጣኖች ጉዳዩ ምንድነው ?ብለው መጠየቅ ሲጀምሩ ጉዳዩ ውስጥ የነበሩበት ባለስልጣኖች ደግሞ የሚይዙት የሚጨብጡት ጠፍቶቸው መተረማመስ ጀመሩ፡፡
..
ግፊት እነ ጫና ሲበዛበት ፖሊስ መግለጫ ሰጠ
ዶ/ር ሰጳራን ያገቷትን ሰዎችን በማደን ላይ አንደሆነና በአሁኑ ጊዜ ፕሮፌሰሩና ሙሉ የተባለው የፕሮፌሰሩ አጋር መሰወራቸውንና ከሀገር ለመውጣት እቅድ እንደነበራቸው መረጃው ስለደረሰው በየትኛውም መንገድ ከሀገር እንዳይወጡ ከፍተኛ ክትትል እየተደረገባቸው እንደሆ ገልፀው ከህብረተሰብም ውስጥ ፕሮፌሰሩንና አጋራቸውን ያሉበን የሚያውቅ ካለ በመጠቆም እንዲተባበር አሳወቁ
//
ዶ/ር ሰጳራና ካሳ በምቹ የሆቴል ክፍል ውስጥ ከታገቱ ሶስት ቀን ሆኗቸዋል፡፡በዚህ ሶስት ቀን ውስጥ ማንም ሰው እኔ ነኝ ያገትኮችሁ ብሎ ያናገራቸው የለም፡፡ግን በራፍቸው ላይ በተጠንቅ 24 ሰዓት የሚጠበብቆቸው ጠባቂዎቻቸው የፈለጉትን ነገሮች ሁሉ ከጥቂት የተከለከሉ እንደሞባይል ያሉ እቃዎች በስተቀር በፍጥነትና ያለማቅማማት ያቀርቡላቸዋል፡፡፡ዶ/ር ምንም እንኳን በመጀመሪያው ቀናቶች የቤተሰቦቾ ነገሮች በጣም እያሳሳባት ስለነበረ እሷ እርፍት አጠጥታ ጠባቂዎቹን በጭቅጭቅ እርፍት ነስታቸው የነበር ቢሆንም ከትናንትና ጀምሮ ግን ቤተሰቦቾ መለቃቸውን እንደውም እናቷንና እህቷን ስለደረሰባቸው ጉዳይ ሲያስረዱ ቀጥታ በቴሊቪዝን ካየች ቡኃላ በጣም ተረጋግታለች፡:፡ካሳ ደግሞ ከመጀመሪያ ቀን አንስቶ እጅግ ደስተኛ ሆኗል፡እንደውም ከከተማ ወጣ ብሎ ሳባና ቢች አካባቢ ባለ ቤርጎ ዘና እያለ ነው ሚመስለው፡፡
ካሳ ከፊት ለፊቷ ተቀምጦ አይን አይኗን እያያት‹‹ዶ/ር እነዚህ ሰዎች ምን ያህል የተባረኩ ናቸው?››አላት
‹‹የእኔ ጅል …የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ እኮ መገደልህ አይቀርም››
‹‹እንዴ ልገደላ …ሞት እኮ መቼም አይቀርልንም…..ግን ይሄው ካንቺ ጋር የሶስት ቀን ገነታዊ የሆነ የጫጉላ ጊዜ እንዳሳልፍ እረድተውኛል...ለእኔ በጣም ባለውለታዬ ናቸው…››
‹‹የጫጉላ ጊዜ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ትርጉሙንም አታውቅም እንዴ?››
‹‹ቀላል ነው ከሚወዶት ሴት ጋር ለብቻ ተገልሎ የብቻ የሆነ ደስታ ጊዜ ማሳለፍ ማለት ነው››
‹‹በቃ››
‹‹አዎ በቃ… ከዛ በላይ ምን አለ?››
‹‹አለ ጂሉ....ለብቻቸው ተገልላው፤ የብቻ ጊዜ ማሳለፋቸው ብቻ ሳይሆን እንዴት እየሳለፉ ነው የሚለውም ወሳኝ ጉዳይ ነው..የጫጉላ ጊዜ ብዙ መሳሳም አለ…መተቃቀፍ አለ..መተሻሸት አለ ፤መዋሰብ አለ..ልጅ መስራት አለ››ከገባው ብላ ዘረዘረቸለት
‹‹በቃ?›አላት በተራው
‹‹ምነው? ልጨምር››
እነዚህን የዘረዘርሻቸው እኮ የፍቅር ማስዋቢያዎች ናቸው...እኔ ደግሞ ፍቅርን በሌሎች ነገሮች መኳኳል አልፈልግም..
እና አሁን እሺ ብዬህ ብንጋባም ምንም አንፈፅምም ማለት ነው?››
‹‹እኔ ብዙም አልፈልግም..ግን አንቺ ምትፈልጊ ከሆነ ችግር የለውም…ወሲብም ሆነ መሳሳሙን ላንቺ ስል አደረገዋለሁ››አላት፤ከእሱ የጠበቀችውን መልስ ነበር ያገኘችው፡፡
‹‹ስለዚህ ይሄንን የጫጉል ጊዜ ላመቻቹልህ ተወዳጆቹ አጋቾችህ ህይወትህን ብትሰጣቸውም ቅር አይልህም ማለት ነው?›አለቺው፡፡
‹‹በትክክል…በተለይ ቆይታችንን ለአንድ ሳማንት ቢያራዝሙልን››
ኣንድ ሰምንት››ዘገነናት…ከዛሬ ነገ ሊገድሉኝ ነው እያሉ የገዛ መሞቻ ጊዜን እየጠበቁ ለአንድ ሳምንት መጠበቅ ከባድ ነው፡፡
‹‹የሆንክ ዊርድ ነገር እኮ ነህ…..ከአንድ ሰው ጋር ዝም ብሎ ለሳምንት ተፋጦ መቀመጠ አያስጨንቅህም?››
‹‹አዎ በጣም ደባሪ ነገር ነው...ከአንድ ሰው ጋር በአንድ ክፍል ውስጥ ለአንድ ቀን እንኳን ተዘግቶብኝ ቢሆን በንዴት እራሴን ላጠፋ ሁሉ እችል ነበር..ችግሩ አንቺ ሌላ ሰው አይደለቺም…..አንቺ ማለት እራሴው ነሽ…ከራሴው ጋ ደግሞ ለዘላለም ብቀመጥ ችግር የለውም››
‹‹አይ አንተ… ጅል አፍቃሪ ነህ እኮ….››አለችና ከተቀመጠችበት ተነስታ ጉንጩን ሳመችው…..ዞር ብላ ወደ መቀመጫዋ ልትመለስ ስትል አይኞቾ ቴሊቭዝኑ ላይ አረፉ… ሪሞቱን አነሳችን ድምፅን ጨምራበት አጠገቧ ያለው ወንበር ላይ ቁጭ ብላ ማየት ጀመረች…ጉዳዩ ሙሉ በሙሉ ስለእነሱ የሚያወራ ስለሆነ ነው ቀልቧን የሳባት፡፡ የሆስፒታላቸው ዋና ባለሼር የሆኑት ሼክ ጠሀ ፊታቸው ለተደረደሩት በቁጥር አምስት ለሚሆኑ ጋዜጠኞች ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጡ ነው፡፡
ክብርን የአትዬጵያ ህዝቦች በሆስፒታላችን ላይ በተከሰተው ጊዜያው ቀውስ በጣም እናዝናለን፡፡ግን እመኑኝ በአጭር ቀናት ውስጥ ከፖሊሶች ጋር በመተባበር በሆስፒታላችን ስም ጀርባ ተሸጉጠው ለአመታት ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩትን ሰዎች በማደን በህግ ተይዘው ፍትህ እንዲሰጣቸው ማድረግ ብቻ ሳይሆን ካለጥፋታቸው በወንጀለኞቹ አሻጥር ሲሳደዱ የነበሩትን ባለደረቦቻችንን ደግሞ በሰላም ወደቤታው እንዲመለሱ ማድረግ ዋና ስራችን ይሆናል፡፡
አንድ ጋዜጠና ማይኩን ወደራሱ አስጠጋና ጥያቄውን ማቅማረብ ጀመረ‹‹ፓሊስ በሰጠው መግለጫ ከሆስፒታሉ ዋና ዋና ባለአክሲዬኖች መካከል ሁለቱ ማለቴ ፕሮፌሰሩና አቶ ሙሉ የተባሉት ግለሰቦች ተሰውረዋል…ታግተዋል የሚሉ ጭምጭምታዎችም አሉ…በዚህ ጉዳይ ላይ ምን አስተያየት አሎት?›
መመለስ ጀመሩ‹‹ፕሮፌሰሩ እና አቶ ሙሉ የሆስፒታሉ ባለአክሲዎኖች ብቻ ሳይሆኑ ሆስፒታሉንም ዋናና ምክትል ሆነው ለአመታት ሲያስተዳድሩ የነበሩ ሰዎች ናቸው.፡፡በሆስፒታሉ የምትከወን እያንዳንዶ ጥቃቅን ነገር ሳትቀር ከእነዚህ ሰዎች እውቅን ውጭ አትከወንም….እና እንደእኔ ግመት እነዚህን ሰዎች ታግተው ሳይሆን ተሸሽገው ወይንም ከሀገር ለመውጣት ሙከራ ላይ ያሉ ይመስለኛል…..ዶ/ር ሰጵራንም አግተዋት ከሆነ በጣም ደጎች ከሆኑ(ፕሮፌሰሩ እጮኛው እንደሆነች ከግምት በማስገባት)ይዘዋት ሊወጡ ይችላሉ…..ካልሆነም አላህ ቸሩን ያሰማን ብቻ……..ግን ፕሮፌሰሩና ግብረ አበሩ ሰሞኑን ከየወዳጆቻቸው ዶላር እየጠየቁ እንደነበር መስማት ችለናል……እቤታቸውም በፖሊስ ሲፈተሸ..ዋና ዋና እቃቸውን በሻንጣ ሞልተው ከቤት እንደወጡ ማወቅ ተችሏል፡፡የሚታገት ሰው ደግሞ እንደዚህ አይደለም›
👍45❤1👎1
ሌላ ጋዜጠኛ‹‹እርሶ የሆስፒታል ትልቅ ባለድርሻ ኖት…ታዲያ ይሄ ሁሉ ውስብስብና አሳዛኝ ወንጀል ሲሰራ እንዴት ዝም ሊሉ ቻሉ?››ሲል መሰረታዊ ሚባል ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡ዶ/ር ሰጳራ በታገተችበት ክፍል ሆና ሼኪው ለዚህ ጥያቄ ምን አይነት መልስ እንደሚመልሱ በጉጉት እየጠበቀች ነው፡፡
ሼኪው መልስ መስጠት ጀመሩ‹‹አይ ልጄ እኔ እንደምታየኝ የዘጠና አምስት አመት ሽማጊሌ ነኝ…ሆስፒታሉን ከባለሞያዎች ጋር ብሬን አውጥቼ ሳቋቁም በመጨረሻ የህይወት ምዕራፌ ለሀገሬና ለህዝቤ መልካም ስራ ለመስራት ካለኝ ፍላጎትና በተጨማሪ ደግሞ ለልጆቼና ለልጅ ልጆቼ ቋሚ ቅርስ ጥያላቸው ለማለፍ ብዬ ነው….አውቃለሁ የሆስፒታሉ ትልቁ ባለድርሻ እኔ ነኝ…ግን ሆስፒታሉ አስተዳደር ላይም ሆነ ሌሎች ስራዎች ላይ ምንም አይነት የቀጥታ ተሳትፎ የለኝም…..ስለሆስፒታሉ መረጃ የማገኘው ከሆስፒታሉ በየሶስት ወሩ እቤቴ ድረስ ከሚልኩልኝ ሪፖርት ነው..ከዛ በስተቀር ያው አዛውንት እንደመሆኔ በሽታ በየጊዜው ነው ሚጎበኘኝ እና እንደማንኛውም ታካሚ ለመታከም እመላለሳለሁ፡፡
‹‹በመጨረሻ የሚያስተላልፉት ነገር አለ?››
አዎ ፕሮፌሰሩና አቶ ሙሉ ተይዘው በህግ ፊት በመቅረብ ለአጠፉት ጠቅላላ ጥፋት መጠየቅ አለባቸው.እነሱን እንድናገኘኝ ለተባበረን ወይም ለፖሊስ ትክክለኛ ጥቆማ ለጠቆመ ሰው 5 ሚሊየን ብር እንሸልማለን…ሌላው የሆስፒተላችን እውቋ ባለሞያ የሆነችውን ዶ/ር ሰጵራን በሰላም እንድትገኝና ከተለጠፈባት የሀሰት ክስ እራሷን ተከላና ጀግና ሰው መሆኗን በህግ ፊት ለመላው ህዝብ አረጋግጣ ወደስራዎ እንድትመለስ እፈልጋለሁ…አዎ እሷ ጠንካራና ብልህ ሴት ስለሆነች በዚህ ሁሉ መከራ ውስጥ አልፋ ለድል እንደምትበቃ እተማመንባታለሁ…ለዚህም አንዲረዳ እኔ በግሌ እሷን በማግኘቱ ለረዳንና ለጠቆመን ሰው ሌላ የ5 ሚሊዬን ብር ሽልማት አዘጋጅቼያለሁ፡፡.በሉ ለዛሬው ይብቃን ሽማግሌ ነኝ ከዚህ በላይ መቀመጡም ይከብደኛል፡››
መግለጫው አለቀ…..ቴሌቪዥን ጣቢያው ቀጥታ አሁናዊው ሁኔታን ማሳየት ጀመረ…. ሰላማዊ ሰልፉ፤ መፈክሩ ተደበላልቆ ይታያል፡፡
ካሳ ሁኔታውን አብሮ ስያይና ሲታዘብ ከቆየ ቡኃላ ‹‹እንዲህ ታወቂ ከሆንሽ ብኃላ ልትገደይ መሆኑ ያሳዝናል፡››አለ
‹‹ እኔ ታዋቂ መሆኔ ሳየሆን የገረመኝ የዚህ ሼኪ እንደዚህ እራሱን ለማንፃት የሄደብት እርቀት ነው ነው ››
‹‹ሰውዬውን ወድጄያቸዋለሁ….ካንቺው ፕሮፌሰር የተሻሉ አራዳ ናቸው›አላት ካሳ
‹‹አንተ ደግሞ በቃ ሁሌ ተቃራኒ ሆኖ ሰውን ማብሸቅ ምኑ ነው የሚያስደስትህ?፡፡
በዚህ መካከል በራፍ ሲጢጢ እያለ መከፈት ጀመረ..ሁለቱም አይናቸውን ወደ በራፉ ወረወሩ፡፡
ካሳ መናገር ጀመረ‹‹አራዳው ሽማጊሌ አሁን ቴሌቪዥን ውስጥ አልነበሩም እንዴ? በየት በየት ዞሮው እኛ ጋር መጡ?››ሲል ጠየቀ፡፡
ዶክተሯም በድንጋጤ እጇን በመዳፎ ላይ አድርጋ‹‹እርሶ እዚህ እንዴት? ››ስትል ተየቀች.
አዛውንቱ አብረቅራቂ ወርቅ ቅብ ከዘራቻን ተደግፈው ወደ ውስጥ የገቡተው በቅርባቸው ያገኙት ወንበር ላይ ተቀመጡና መናገር ጀመሩ‹‹ዶክተር ባለፉት ሶስት ቀናት ውስጥ የእኔ ሰዎች እንክብካቤ እንዳላጎደሉባችሁ እርግጠኛ ነኝ››
‹‹እና እርሶ ኖት ያሳገቱን?››
‹‹ዶክተር አንዴት እንደምወድሽና እንዴት እንደማከብርሽ ታውቂያለሽ….መታገት የሚል ከባድ ቃል ስትጠቀሚ ስሰማ ይከፋኛል…እኔ ሊገድልሽ ከነበረ የገዛ እጮኛሽ ነው ያዳንኩሽ…እዚህም ከጓደኞችሽ ጋር ያመጣሁሽ ና ያቆየሁሽ ከአደጋ ነፃ መሆንሽን እርግጠኛ አስከምሆን ነው፡፡እጮኛሽም ሆነ በፖሊሶች እጅ እንዳትገቢ አንቺን ለመጠበቅ ያደረኩት ነው››
‹‹ምንም አይደል፡፡››
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
ሼኪው መልስ መስጠት ጀመሩ‹‹አይ ልጄ እኔ እንደምታየኝ የዘጠና አምስት አመት ሽማጊሌ ነኝ…ሆስፒታሉን ከባለሞያዎች ጋር ብሬን አውጥቼ ሳቋቁም በመጨረሻ የህይወት ምዕራፌ ለሀገሬና ለህዝቤ መልካም ስራ ለመስራት ካለኝ ፍላጎትና በተጨማሪ ደግሞ ለልጆቼና ለልጅ ልጆቼ ቋሚ ቅርስ ጥያላቸው ለማለፍ ብዬ ነው….አውቃለሁ የሆስፒታሉ ትልቁ ባለድርሻ እኔ ነኝ…ግን ሆስፒታሉ አስተዳደር ላይም ሆነ ሌሎች ስራዎች ላይ ምንም አይነት የቀጥታ ተሳትፎ የለኝም…..ስለሆስፒታሉ መረጃ የማገኘው ከሆስፒታሉ በየሶስት ወሩ እቤቴ ድረስ ከሚልኩልኝ ሪፖርት ነው..ከዛ በስተቀር ያው አዛውንት እንደመሆኔ በሽታ በየጊዜው ነው ሚጎበኘኝ እና እንደማንኛውም ታካሚ ለመታከም እመላለሳለሁ፡፡
‹‹በመጨረሻ የሚያስተላልፉት ነገር አለ?››
አዎ ፕሮፌሰሩና አቶ ሙሉ ተይዘው በህግ ፊት በመቅረብ ለአጠፉት ጠቅላላ ጥፋት መጠየቅ አለባቸው.እነሱን እንድናገኘኝ ለተባበረን ወይም ለፖሊስ ትክክለኛ ጥቆማ ለጠቆመ ሰው 5 ሚሊየን ብር እንሸልማለን…ሌላው የሆስፒተላችን እውቋ ባለሞያ የሆነችውን ዶ/ር ሰጵራን በሰላም እንድትገኝና ከተለጠፈባት የሀሰት ክስ እራሷን ተከላና ጀግና ሰው መሆኗን በህግ ፊት ለመላው ህዝብ አረጋግጣ ወደስራዎ እንድትመለስ እፈልጋለሁ…አዎ እሷ ጠንካራና ብልህ ሴት ስለሆነች በዚህ ሁሉ መከራ ውስጥ አልፋ ለድል እንደምትበቃ እተማመንባታለሁ…ለዚህም አንዲረዳ እኔ በግሌ እሷን በማግኘቱ ለረዳንና ለጠቆመን ሰው ሌላ የ5 ሚሊዬን ብር ሽልማት አዘጋጅቼያለሁ፡፡.በሉ ለዛሬው ይብቃን ሽማግሌ ነኝ ከዚህ በላይ መቀመጡም ይከብደኛል፡››
መግለጫው አለቀ…..ቴሌቪዥን ጣቢያው ቀጥታ አሁናዊው ሁኔታን ማሳየት ጀመረ…. ሰላማዊ ሰልፉ፤ መፈክሩ ተደበላልቆ ይታያል፡፡
ካሳ ሁኔታውን አብሮ ስያይና ሲታዘብ ከቆየ ቡኃላ ‹‹እንዲህ ታወቂ ከሆንሽ ብኃላ ልትገደይ መሆኑ ያሳዝናል፡››አለ
‹‹ እኔ ታዋቂ መሆኔ ሳየሆን የገረመኝ የዚህ ሼኪ እንደዚህ እራሱን ለማንፃት የሄደብት እርቀት ነው ነው ››
‹‹ሰውዬውን ወድጄያቸዋለሁ….ካንቺው ፕሮፌሰር የተሻሉ አራዳ ናቸው›አላት ካሳ
‹‹አንተ ደግሞ በቃ ሁሌ ተቃራኒ ሆኖ ሰውን ማብሸቅ ምኑ ነው የሚያስደስትህ?፡፡
በዚህ መካከል በራፍ ሲጢጢ እያለ መከፈት ጀመረ..ሁለቱም አይናቸውን ወደ በራፉ ወረወሩ፡፡
ካሳ መናገር ጀመረ‹‹አራዳው ሽማጊሌ አሁን ቴሌቪዥን ውስጥ አልነበሩም እንዴ? በየት በየት ዞሮው እኛ ጋር መጡ?››ሲል ጠየቀ፡፡
ዶክተሯም በድንጋጤ እጇን በመዳፎ ላይ አድርጋ‹‹እርሶ እዚህ እንዴት? ››ስትል ተየቀች.
አዛውንቱ አብረቅራቂ ወርቅ ቅብ ከዘራቻን ተደግፈው ወደ ውስጥ የገቡተው በቅርባቸው ያገኙት ወንበር ላይ ተቀመጡና መናገር ጀመሩ‹‹ዶክተር ባለፉት ሶስት ቀናት ውስጥ የእኔ ሰዎች እንክብካቤ እንዳላጎደሉባችሁ እርግጠኛ ነኝ››
‹‹እና እርሶ ኖት ያሳገቱን?››
‹‹ዶክተር አንዴት እንደምወድሽና እንዴት እንደማከብርሽ ታውቂያለሽ….መታገት የሚል ከባድ ቃል ስትጠቀሚ ስሰማ ይከፋኛል…እኔ ሊገድልሽ ከነበረ የገዛ እጮኛሽ ነው ያዳንኩሽ…እዚህም ከጓደኞችሽ ጋር ያመጣሁሽ ና ያቆየሁሽ ከአደጋ ነፃ መሆንሽን እርግጠኛ አስከምሆን ነው፡፡እጮኛሽም ሆነ በፖሊሶች እጅ እንዳትገቢ አንቺን ለመጠበቅ ያደረኩት ነው››
‹‹ምንም አይደል፡፡››
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍29🥰7😁2❤1🤔1
የተሰባበሩ ነፍሶች
ምዕራፍ_17
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
""""
ካሳና ዶ/ር ሶፊያ በታገቱበት ቢት ሼኪው ተከስተዋል፡፡
"ሼኪ እሶን አይስሞት ...በእውነቱ ድንቅ መስተንግዶ ነው የተደረገልን ...እንደው ካላስቸገርኮት አንድ ወር ወይም አንድ ሳምንት በተመሳሳይ ሁኔታ ብንቆይ ውለታዋትን አንረሳውም።"አለ ካሳ፡፡
የካሳን እጅ እግር የሌለው ወሬ ችላ ብላ"ቆይ ያ አውሬ እቤተሠቦቼን እንዴት ሊለቃቸው ቻለ?"ስትል ጠየቀች።
"ተገዶ"አሏት በአጭሩ
"አልገባኝም...እርሷ ኖት ያስገደድት?ምን ለማግኘት ብለው?"
"እኔ አይደለሁም .....ቢሆን ደስ ይለኝ ነበር ...በአንቺ ዘንድ ሌላ ውለታ ሆኖ ይመዘገብልኝ ነበር"
"እና ሌላ ማን ነው?የህዝብን ጩኸትና ሠላማዊ ሰልፍን ፈርቶ"
‹‹አሁን ያንቺ ሰውዬ ነው የህዝብ ጩኸት ፈርቶ እንደዚህ አይነት ነገር የሚያደርገው ደግሞስ እንደምታውቂው ይሄ ህዝብ ዝምብ ነው..አንዳንዴ የሰማውን ነገር እንኳን ለምን ብሎ ሳያጣራ ግር ብሎ መጥቶ አካባቢሽን ሲወረው ..እሽ ብለሽ ታባርሪዋለሽ…አልሰማ ሲልሽና ትንሽ ሲያበሳጭሽ..እጅሽን አስወንጭፈሽ በአየር ላይ ቀጨም ታደርጊውና በመዳፍሽ ውስጥ አፍነሽ ትጨፈልቂዋለሽ…..በቃ ጭፍልቅ…፡፡ከዛ የተጨበጠ የእጅ መዳፍሽን ታላቅቂና እሬሳውን ከእጅሽ ላይ አራግፈሽ ወደቆሻሸ ማጠራቀሚያ ትጨምሪዋለሽ…እጅሽን በንፅህ ውሀና በሳሙና ፈትገሽ በማታጠብ እራስሽን ታፀጂና የተለመደ ተግባርሽን መከወንሽን ትቀጥያለሽ፡፡አዎ ህዝብ እና ዝንብ አንድ ናቸው፡፡
‹‹እና እርሶም እንደዛ ነው የሚያስቡት››
‹‹አዎ በዚህ ጉዳይ እንኳን ከፕሮፌሰሩ ጋር ልዩነት የለኝ››
‹‹እኔ እስከማውቀው ግን በሌሎችም ጉዳዬች ላይ ከእሱ ጋር ልዩነት ሲኖራችሁ አይቼ አላውቅም….ጥሩ አባትና ልጅ ነው የምትመስሉት..ሁለታችሁም የዳቢሎስ ልብ ነው ያላችሁ››
‹‹ተይ እንጂ ዶክተር…..እኔን ከእጮኛሽ ጋር በጭካኔ ማነፃፀር ምን አይነት ፍርደ ገምድልነት ነው?››
"አሁን እሱን ተውትና የጠየቅኮትን ይመልሱልኝ፤ ቤተሰቦቼን ለምን እንደለቀቃቸው ምክንያቱን አያውቁም ማለት ነው?።"
"አውቃለሁ የራስሽ ልጅ ነው?"
"አልገባኝም"
"አቢዬት"
"እንዴት አድርጓ ?የት አግኝቶት? ማለት መሠወሩን በዜና ሰምቼ ነበር"
"ተሠውሮ አይደለም ታግቶ ነው...ያንቺ አብዬት አንቺው በታገትሽበት ምሽት ነው አግቶ ቤተሰቦችሽን እንዲለቅ ያደረገው...እሱን ብቻ ሳይሆን ሙሉንም አግቶታል። ምን አልባት እኔንም ሞክሮ ሳይሳካለት ቀርቶ ሊሆን ይችላል.....አሁን ሁለቱም በእሱ እጅ ናቸው።"
"የእኔ ጀግና"እንባዎ በጉንጮቾ ተንኳለለ።
"ያ አውሬ ተሣካለት…አሁን ሁለት ተፎካካሪዎቼ አንድ ቤት ናቸው...እንደው ሼኪ እሷን እዚህ አስቀርተው እኔን ቢለቁኝና ብቀላቀላቸው።"አለ ካሳ በሰማው ነገር ተበሳጭቶ...የዶተሯ አዳኝ ጀግና ከእሱ ውጭ ሌላ ሰው እንዲሆን አይፈልግም።በተለይ አፍቃሪዎቾ እንዲሆኑ።
ሼኪው የሚናገረው ስላልገባቸው "የምን ተፎካካሪ?"ሲሉ ጠየቁት
"ሦስታችንም የእሷ ፍቅር ተጠቂዎች ነን...እርስ በርስ ደግሞ ጣውንታሞች።
"እ እንደዛ ነው"
ዶ/ሯ ትግስቷ አልቆ ‹‹ሼኪ አሁን በዚህ ሰዓት ከእሱ ጋር ያወራሉ ...እሺ አሁን የእርሷ ዕቅድ ምንድነው?ምን ሊያደርጉን ነው ያሰብት?"
"አመጣጤ እኮ ስለዛው ልነግርሽ ነበር?"ብለው በከዘራቸው በመረዳት ከመቀመጫቸው ተነስተው ቆሙና"ዶ/ር ስለእናንተ ጉዳይ ከአብዬት ጋር እየተደራደርን ነው ...ቁርጥ ያለ ስምምነት ላይ ስንደርስ እንድታውቂው ይደረጋል።"
"በምንድነው የምትደራደሩት ፤እነዛን አራጅ ወንጀለኞችን ለማስለቀቅ?እነሡ ተለቀው ከተጠያቂነት ከሚያመልጡ እኔ አዚሁ የሆንኩትን ብሆን ይሻለኛል"
ፊታቸውን ዞረው እግራቸውን እየጎተቱ ወደ መውጫው መጓዝ ጀመሩ
"ጥያቄዬን መልሱልኝ እንጂ"
"ነገርኩሽ ዶ/ር ...ስምምነቱ ሲጠናቀቅ እንድታውቂው ይደረጋል" አሉና በራፋን ቆረቆሩ ፤ከውጭ ያለው ጠባቂ ከፈተላቸው።ወጥተው ሄድ።
እሷ በቆመችበት ተንገዳገደች...እራሷን ለመቆጣጠር ብትሞክርም አልቻለችም....ተዝለፍልፍ ወደቀች።
"እንዴ ዶክተር ደስታ ነው ወይስ ዋቴ ሰርተሽ እንዲለቁሽ እየሞከርሽ ነሽ።"አለ ካሳ ሁኔታዋ ግራ አጋብቶት።
መልስ ሲያጣ ከመቀመጫው ተነሳና ተጠጋት.. ቁጢጥ አለና ወዘወዛት ..አትንቀሳቀስም ሰቅስቋ በማቀፍ አልጋ ላይ አስተኛትና በሩን ሄዶ በሀይል አንኳኳ ።ጠባቂው መጥቶ ከፈተ
"ምን ተፈጠረ.?"
"ራሷን ሳተች"
"ራሳን ስተች ማለት?" ሁለቱም ተጠ ጓት.... ጠባቂው ዝቅ ብሎ ትንፋሿን አዳመጠ...ፈጠን ብሎ ጠረጰዛ ላይ ያለ የውሀ ጆግ አነሳና በጨርቅ እየነከረ ያቀዘቅዝላት ጀመር ...ከሶስት ደቂቃ ብኃላ ነቃች
"ምን ሆኜ ነው?"
"በደስታ እራስሽን ስተሽ"ካሳ ነው የመለሰላት፡፡
"ምንድነው የምትቀባዠረው?የምን ደስታ ነው"ጮኸችበት።
ጠበቂው"ዶ/ር ተረጋጊ ...ስለተጨናነቅሽ ይሆናል እራስሽን የሳትሽው።"
"የሄንን ሁሉ ትህትና ይዘህ የወንጀለኛ ጉዳይ አስፈፃሚ መሆን አይከብድም?"አለችው፤ ከመጀመሪያው ቀን አንስቶ እያሳያቸው በነበረው ትህትናና ስርአት ያለው መስተንግዶ ተገርማ፡፡
"ዶ/ር ህይወት ከበድ እንደሆነች መቼስ ለአንቺ አልነግርሽም...አንዳንዴ ገነት ያደርሰኛል ብለሽ የጀመርሽው መንገድ በየት አዙሩ ሲኦል እንደሚጥልሽ አታውቂም።"አለና ከተቀመጠበት ተነሳና ቆመ..
"እንደው አንድ ነገር ላስቸግርህ?"
"ምችለው ከሆነ ችግር የለም"
"አንድ ቦታ ለመደወል ስልክ ፈልጌ ነበር"
"በራሴ እንደዛ ማድረግ አልችልም..ታውቂያለሽ በራፍ ላይ ሁኔታዎችን የሚቆጣጠር ሌላ ጠባቂ አለ..ማድረግ የምችለው ሀለቃዬ ጋር ደውዬ ሀኪም እንደሚያስፈልግሽና ስልክም እንደጠየቅሺኝ ነግራቸዋለሁ..ከዛ መልሱን አሳውቅሻለሁ።"ብሎ ወጥቶ ሊሄድ በራፍ አቅራቢያ ሲደርስ ቆይ አንዴ ብላ አስቆመችው።
ኮመዲኖ ላይ ካለው ማስታወሻ አንድ ሉክ ቀደደችና
አብዬት እኔን ለማስለቀቅ ከሼኪው ጋር እየተደራደርክ መሆኑን አውቃለሁ። በምንም አይነት እኔን ለማዳን ብለህ እነዣ ሰው በላ ጭራቆች እንዲያመልጡና ነፃ እንዲወጡ እንዳታደርግ..እኔን ባለሁበት ተወኝ...እነሱ በአደባባይ እንዲሰቀሉና ሰማንያ ቦታ እንዲቆራረጡ ነው የምፈልገው።ደግሞ ቤተሠቦቼን በሰላም ወደቤታቸው እንዲመለሡ ስላደረክ አመሠግናለሁ።በጣም ነው የምወድህ።"
ስልክ.ቁ 091205....ፅፋ ከጨረሰች ብኃላ።
በዚህ ቁጥር ደውልና ለሚያነሳው ሰው ይሄንን መልዕክት ንገርልኝ።አውቃለሁ ትልቅ ውለታ እየጠየኩህ ነው...እባክህ "
እሺም እንቢም ሳይል ወረቀቱን ተቀብሏት ኪሱ ውስጥ ጨመረና በራፍን በላያቸው ላይ መልሶ ከውጭ በመቆለፍ ሄደ።
"አይገርምሽም ዶ/ር እነዚህን ሠዎች በጣም ነው የወደድኳቸው..."ካሳ ነው ተናጋሪው፡፡
"ሂድና ሳማቸዋ"
"እኔ የወደድኩትን ስስም አይተሽ ታውቂያለሽ? ለምሳሌ አንቺን ስሜሽ አውቃለሁ?"
ምንም አልመለሠችለትም… ከላይ ያለበሰችውን አልጋልብስ ወደላይ ሳበችና ሙሉ በሙሉ ፊቷን ሸፍነች። እንቅልፏ መጥቶ አልነበረም። በፀጥታ በካሳ አንጀት አድብን ንግግሮች ሳትረበሽ ለማሰብ እንጂ"
እሱም ወደሌላው አልጋ ሄዶ ከእነጫማው ወጣና ተዘርሮ ተኛ...በደቂቃ ውስጥ ነበር ጭልጥ ያለ እንቅልፍ የወሰደው።
////
አብት ከአቶ ሙሉ ፊት ለፊት ቁጭ ብሎ እየተደራደረው ነው፡፡
<<አቶ ሙሉ የነገርኩህን ነገር አሰብክበት?››
‹አዎ አሰቤበታለሁ… .ግን ምን መሰለህ እባክህ ከዚህ ጉድ አውጣኝ..ወደውጭ እንድወጣ ከረዳሀኝ ግማሽ ሀብቴን ላስተላልፍልህ እችላለሁ››
‹‹ግማሽ ሀብትህ ምን ያህል ይሆናል?››
‹‹እስከ 20 ሚሊዬን››
ምዕራፍ_17
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
""""
ካሳና ዶ/ር ሶፊያ በታገቱበት ቢት ሼኪው ተከስተዋል፡፡
"ሼኪ እሶን አይስሞት ...በእውነቱ ድንቅ መስተንግዶ ነው የተደረገልን ...እንደው ካላስቸገርኮት አንድ ወር ወይም አንድ ሳምንት በተመሳሳይ ሁኔታ ብንቆይ ውለታዋትን አንረሳውም።"አለ ካሳ፡፡
የካሳን እጅ እግር የሌለው ወሬ ችላ ብላ"ቆይ ያ አውሬ እቤተሠቦቼን እንዴት ሊለቃቸው ቻለ?"ስትል ጠየቀች።
"ተገዶ"አሏት በአጭሩ
"አልገባኝም...እርሷ ኖት ያስገደድት?ምን ለማግኘት ብለው?"
"እኔ አይደለሁም .....ቢሆን ደስ ይለኝ ነበር ...በአንቺ ዘንድ ሌላ ውለታ ሆኖ ይመዘገብልኝ ነበር"
"እና ሌላ ማን ነው?የህዝብን ጩኸትና ሠላማዊ ሰልፍን ፈርቶ"
‹‹አሁን ያንቺ ሰውዬ ነው የህዝብ ጩኸት ፈርቶ እንደዚህ አይነት ነገር የሚያደርገው ደግሞስ እንደምታውቂው ይሄ ህዝብ ዝምብ ነው..አንዳንዴ የሰማውን ነገር እንኳን ለምን ብሎ ሳያጣራ ግር ብሎ መጥቶ አካባቢሽን ሲወረው ..እሽ ብለሽ ታባርሪዋለሽ…አልሰማ ሲልሽና ትንሽ ሲያበሳጭሽ..እጅሽን አስወንጭፈሽ በአየር ላይ ቀጨም ታደርጊውና በመዳፍሽ ውስጥ አፍነሽ ትጨፈልቂዋለሽ…..በቃ ጭፍልቅ…፡፡ከዛ የተጨበጠ የእጅ መዳፍሽን ታላቅቂና እሬሳውን ከእጅሽ ላይ አራግፈሽ ወደቆሻሸ ማጠራቀሚያ ትጨምሪዋለሽ…እጅሽን በንፅህ ውሀና በሳሙና ፈትገሽ በማታጠብ እራስሽን ታፀጂና የተለመደ ተግባርሽን መከወንሽን ትቀጥያለሽ፡፡አዎ ህዝብ እና ዝንብ አንድ ናቸው፡፡
‹‹እና እርሶም እንደዛ ነው የሚያስቡት››
‹‹አዎ በዚህ ጉዳይ እንኳን ከፕሮፌሰሩ ጋር ልዩነት የለኝ››
‹‹እኔ እስከማውቀው ግን በሌሎችም ጉዳዬች ላይ ከእሱ ጋር ልዩነት ሲኖራችሁ አይቼ አላውቅም….ጥሩ አባትና ልጅ ነው የምትመስሉት..ሁለታችሁም የዳቢሎስ ልብ ነው ያላችሁ››
‹‹ተይ እንጂ ዶክተር…..እኔን ከእጮኛሽ ጋር በጭካኔ ማነፃፀር ምን አይነት ፍርደ ገምድልነት ነው?››
"አሁን እሱን ተውትና የጠየቅኮትን ይመልሱልኝ፤ ቤተሰቦቼን ለምን እንደለቀቃቸው ምክንያቱን አያውቁም ማለት ነው?።"
"አውቃለሁ የራስሽ ልጅ ነው?"
"አልገባኝም"
"አቢዬት"
"እንዴት አድርጓ ?የት አግኝቶት? ማለት መሠወሩን በዜና ሰምቼ ነበር"
"ተሠውሮ አይደለም ታግቶ ነው...ያንቺ አብዬት አንቺው በታገትሽበት ምሽት ነው አግቶ ቤተሰቦችሽን እንዲለቅ ያደረገው...እሱን ብቻ ሳይሆን ሙሉንም አግቶታል። ምን አልባት እኔንም ሞክሮ ሳይሳካለት ቀርቶ ሊሆን ይችላል.....አሁን ሁለቱም በእሱ እጅ ናቸው።"
"የእኔ ጀግና"እንባዎ በጉንጮቾ ተንኳለለ።
"ያ አውሬ ተሣካለት…አሁን ሁለት ተፎካካሪዎቼ አንድ ቤት ናቸው...እንደው ሼኪ እሷን እዚህ አስቀርተው እኔን ቢለቁኝና ብቀላቀላቸው።"አለ ካሳ በሰማው ነገር ተበሳጭቶ...የዶተሯ አዳኝ ጀግና ከእሱ ውጭ ሌላ ሰው እንዲሆን አይፈልግም።በተለይ አፍቃሪዎቾ እንዲሆኑ።
ሼኪው የሚናገረው ስላልገባቸው "የምን ተፎካካሪ?"ሲሉ ጠየቁት
"ሦስታችንም የእሷ ፍቅር ተጠቂዎች ነን...እርስ በርስ ደግሞ ጣውንታሞች።
"እ እንደዛ ነው"
ዶ/ሯ ትግስቷ አልቆ ‹‹ሼኪ አሁን በዚህ ሰዓት ከእሱ ጋር ያወራሉ ...እሺ አሁን የእርሷ ዕቅድ ምንድነው?ምን ሊያደርጉን ነው ያሰብት?"
"አመጣጤ እኮ ስለዛው ልነግርሽ ነበር?"ብለው በከዘራቸው በመረዳት ከመቀመጫቸው ተነስተው ቆሙና"ዶ/ር ስለእናንተ ጉዳይ ከአብዬት ጋር እየተደራደርን ነው ...ቁርጥ ያለ ስምምነት ላይ ስንደርስ እንድታውቂው ይደረጋል።"
"በምንድነው የምትደራደሩት ፤እነዛን አራጅ ወንጀለኞችን ለማስለቀቅ?እነሡ ተለቀው ከተጠያቂነት ከሚያመልጡ እኔ አዚሁ የሆንኩትን ብሆን ይሻለኛል"
ፊታቸውን ዞረው እግራቸውን እየጎተቱ ወደ መውጫው መጓዝ ጀመሩ
"ጥያቄዬን መልሱልኝ እንጂ"
"ነገርኩሽ ዶ/ር ...ስምምነቱ ሲጠናቀቅ እንድታውቂው ይደረጋል" አሉና በራፋን ቆረቆሩ ፤ከውጭ ያለው ጠባቂ ከፈተላቸው።ወጥተው ሄድ።
እሷ በቆመችበት ተንገዳገደች...እራሷን ለመቆጣጠር ብትሞክርም አልቻለችም....ተዝለፍልፍ ወደቀች።
"እንዴ ዶክተር ደስታ ነው ወይስ ዋቴ ሰርተሽ እንዲለቁሽ እየሞከርሽ ነሽ።"አለ ካሳ ሁኔታዋ ግራ አጋብቶት።
መልስ ሲያጣ ከመቀመጫው ተነሳና ተጠጋት.. ቁጢጥ አለና ወዘወዛት ..አትንቀሳቀስም ሰቅስቋ በማቀፍ አልጋ ላይ አስተኛትና በሩን ሄዶ በሀይል አንኳኳ ።ጠባቂው መጥቶ ከፈተ
"ምን ተፈጠረ.?"
"ራሷን ሳተች"
"ራሳን ስተች ማለት?" ሁለቱም ተጠ ጓት.... ጠባቂው ዝቅ ብሎ ትንፋሿን አዳመጠ...ፈጠን ብሎ ጠረጰዛ ላይ ያለ የውሀ ጆግ አነሳና በጨርቅ እየነከረ ያቀዘቅዝላት ጀመር ...ከሶስት ደቂቃ ብኃላ ነቃች
"ምን ሆኜ ነው?"
"በደስታ እራስሽን ስተሽ"ካሳ ነው የመለሰላት፡፡
"ምንድነው የምትቀባዠረው?የምን ደስታ ነው"ጮኸችበት።
ጠበቂው"ዶ/ር ተረጋጊ ...ስለተጨናነቅሽ ይሆናል እራስሽን የሳትሽው።"
"የሄንን ሁሉ ትህትና ይዘህ የወንጀለኛ ጉዳይ አስፈፃሚ መሆን አይከብድም?"አለችው፤ ከመጀመሪያው ቀን አንስቶ እያሳያቸው በነበረው ትህትናና ስርአት ያለው መስተንግዶ ተገርማ፡፡
"ዶ/ር ህይወት ከበድ እንደሆነች መቼስ ለአንቺ አልነግርሽም...አንዳንዴ ገነት ያደርሰኛል ብለሽ የጀመርሽው መንገድ በየት አዙሩ ሲኦል እንደሚጥልሽ አታውቂም።"አለና ከተቀመጠበት ተነሳና ቆመ..
"እንደው አንድ ነገር ላስቸግርህ?"
"ምችለው ከሆነ ችግር የለም"
"አንድ ቦታ ለመደወል ስልክ ፈልጌ ነበር"
"በራሴ እንደዛ ማድረግ አልችልም..ታውቂያለሽ በራፍ ላይ ሁኔታዎችን የሚቆጣጠር ሌላ ጠባቂ አለ..ማድረግ የምችለው ሀለቃዬ ጋር ደውዬ ሀኪም እንደሚያስፈልግሽና ስልክም እንደጠየቅሺኝ ነግራቸዋለሁ..ከዛ መልሱን አሳውቅሻለሁ።"ብሎ ወጥቶ ሊሄድ በራፍ አቅራቢያ ሲደርስ ቆይ አንዴ ብላ አስቆመችው።
ኮመዲኖ ላይ ካለው ማስታወሻ አንድ ሉክ ቀደደችና
አብዬት እኔን ለማስለቀቅ ከሼኪው ጋር እየተደራደርክ መሆኑን አውቃለሁ። በምንም አይነት እኔን ለማዳን ብለህ እነዣ ሰው በላ ጭራቆች እንዲያመልጡና ነፃ እንዲወጡ እንዳታደርግ..እኔን ባለሁበት ተወኝ...እነሱ በአደባባይ እንዲሰቀሉና ሰማንያ ቦታ እንዲቆራረጡ ነው የምፈልገው።ደግሞ ቤተሠቦቼን በሰላም ወደቤታቸው እንዲመለሡ ስላደረክ አመሠግናለሁ።በጣም ነው የምወድህ።"
ስልክ.ቁ 091205....ፅፋ ከጨረሰች ብኃላ።
በዚህ ቁጥር ደውልና ለሚያነሳው ሰው ይሄንን መልዕክት ንገርልኝ።አውቃለሁ ትልቅ ውለታ እየጠየኩህ ነው...እባክህ "
እሺም እንቢም ሳይል ወረቀቱን ተቀብሏት ኪሱ ውስጥ ጨመረና በራፍን በላያቸው ላይ መልሶ ከውጭ በመቆለፍ ሄደ።
"አይገርምሽም ዶ/ር እነዚህን ሠዎች በጣም ነው የወደድኳቸው..."ካሳ ነው ተናጋሪው፡፡
"ሂድና ሳማቸዋ"
"እኔ የወደድኩትን ስስም አይተሽ ታውቂያለሽ? ለምሳሌ አንቺን ስሜሽ አውቃለሁ?"
ምንም አልመለሠችለትም… ከላይ ያለበሰችውን አልጋልብስ ወደላይ ሳበችና ሙሉ በሙሉ ፊቷን ሸፍነች። እንቅልፏ መጥቶ አልነበረም። በፀጥታ በካሳ አንጀት አድብን ንግግሮች ሳትረበሽ ለማሰብ እንጂ"
እሱም ወደሌላው አልጋ ሄዶ ከእነጫማው ወጣና ተዘርሮ ተኛ...በደቂቃ ውስጥ ነበር ጭልጥ ያለ እንቅልፍ የወሰደው።
////
አብት ከአቶ ሙሉ ፊት ለፊት ቁጭ ብሎ እየተደራደረው ነው፡፡
<<አቶ ሙሉ የነገርኩህን ነገር አሰብክበት?››
‹አዎ አሰቤበታለሁ… .ግን ምን መሰለህ እባክህ ከዚህ ጉድ አውጣኝ..ወደውጭ እንድወጣ ከረዳሀኝ ግማሽ ሀብቴን ላስተላልፍልህ እችላለሁ››
‹‹ግማሽ ሀብትህ ምን ያህል ይሆናል?››
‹‹እስከ 20 ሚሊዬን››
👍32
‹‹እና 20 ሚሊዬን ልትሰጠኝ?››
እንደነገርከኝ ከሆነ እስከአሁን የ205 ሰዎች ኩላሊት በጥቂት ገንዘብ እየገዛችሁ አንዳንዱንም በአደጋ ሆስፐታል ከገብና ከሞቱ ሰዎች ሰርቃችሁ ሸጣችሆል፡፡የ52 ሰዎች ልብ ሸጣችኋል፡..ሌላም ብዙ ብዙ የሚዘገንኑ ወንጀሎች››
‹‹አዎ.ብዙ ጊዜ እኮ ያልካቸውን ወንጀሎች መፈፀማችንን ነግሬሀለው››
‹‹ምነው ታዲያ ስትፈፅሙት ያልደከማችሁ አሁን ስታወራው አንገሸገሸህ፤ስማኝ ከጠቀስክልኝ ወንጀሎች ውስጥ ቢያንስ ግማሹ በእናንተ ታፍነው ልባቸውና በመዝረፍ እንዲሞቱና ሰውነታቸው በአሲድ ቀልጦ ለቀብር እንኳን እንዳይበቁ የተደረጉ ናቸወ፡..እና 20ሚሊዬን ሳይሆን 20 ቢሊዬን ብር ቢኖርህና እንኳን አያድንህም››
‹‹ግን የዚህ ሀሳብ ጠንሳሽም ዋናው አድራጊ ፈጣሪ እኮ ፕሮፌሰሩ ነው፡፡የእኔና የሺኪው ድርሻ ትንሽ ነው››በማለት እራሱን ለመከላከል ሚያደርገውን ጥረት ቀጠለበት፡፡
በንግግሩ አብዬት ተንቀጠቀጠ‹‹ግን ምን አይነት ህሊና ቢስ ሰው ነህ?እንዚህን ቃላቶች ከአንደበትህ ስታወጣ ትንሽ አያደናቅፍህም?ስማ እኔ የእድሜዬን ግማሽ ማጅራት መቺ ሆኜ አሳልፌያለሁ ፡፡በዚህ ሂደት በስህተት አንድ ሰው በእጄ ላይ አልፎል እና ከዛን ቀን ጀምሮ ንፅህ እንቅልፍ ተኝቼ አላውቅም… እናንተ ያን ሁሉ ሰው እንዲህ ጨፈጭፋችሁ እንዴት ነው በሰላም መተንፈስ የምትችሉት..ምን አይት አውሬነት ነው በውስጣችሁ ያለው?፡፡አሁን ዝም ብለህ ስማኝ …እኔ እናንተን ለመንግስት አሳልፌ ሰጥቼ በ ፍርድ ቤት እስክትዳኙ መጠበቅ እልችልም፡፡ምን አልባትም የሞት ፍርድም ቢፈረድባችሁ አንኳን አያረካኝም››
‹‹እሸ እንዲሆን የምትፈልገውን ንገረኝ?››
‹‹ኩላሊታቸው ለተዘረፉ 35 ሰዎችን ማግኘት ችለናል.እንሱ አንድ ላይ ሆነው ጠበቃ ገዝተው ሆስፒታላችሁን ከሰዋል፡፡እርግጠኛነኝ ፍርድቤቱ ተገቢውን ካሳ ስለሚበይንላቸው የሚከፈለው ከአንተና ከፕሮፌሰሩ ሼር ተቀንሶ ነው፡፡
‹እንዴ ሼኪውስ…ከዚህ ጉዳይ ከተገኘ አያንዳንዱ ትርፍ ተካፋይ ነበሩ እኮ…››
‹‹ጥሩ .ለጊዜው ግን እሳቸውና ዶዬ እዚህ ወንጀል ውስጥ አይካቱም.. ለአንተ ቤተሰብ የሚሰጠውን ብር ከእሳቸው ነው የምቀበለው….በዛ ላይ ዶክተሯና ጓደኛዬ በእሳቸው እጅ ነው ያሉት..ግን እመነኝ ቀኑ ሲደርስ እራሴው ለሰሩት ወንጀል በደንብ አስከፍላቸዋለው ለዛ ቃል ገባልሀለሁ፡፡አንተ ግን ስለሆስፒታሉ ሼር እርሳው.ምንም አይኖርህም፡፡››
‹‹ቤተሰቦቼ እዚህ ወንጀል ውስጥ የሉበትም.ሚስቴ በጣም ሀይማኖተኛ ና ፈርሀ እግዚያብሄር ያላት ሴት ነች .እና በእኔ ሀጥያት እነሱ መቀጣት የለባቸውም.እንድ ያላቸው መተዳደሪያ ደግሞ ይሄ ሆስፒታል የሚገኝ ገቢ ነው››
‹‹እሱን እኮ አየሁ… ሚስትህንም ልጆችህንም አነጋግሬያቸዋለሁ….ስለአንተ በሚዲያም በሰሙት ነገር ተሳቀውና ተሸማቀው ነው ያሉት…..ብትሞት እራሱ ያን ያህል አያዝኑም…እንዴት አንተን የመሰለ የሰይጣን ታናሽ ወንድም እዛ ቤተሰብ ውስጥ ሊኖር እንደቻላ ማሰብ እንኳን አልቻልኩም፡፡
‹‹አዝናለሁ››
‹‹አይ አንተማ ሀዘኔታ የሚባል ነገር ውስጥህ የለም..ይልቅ አሁን ስማኝ…ለቤተሰብ 20 ሚሊየን ጥሬ በር እንዲደርሰቸው አደርጋለው፡ያንን በስልክ እንድታረጋግጥ ይደረጋል፤ከዛ ቡኃላ ግን ያልከሀውን ታደርጋለህ›
በመጀመሪያ የእያንዳንዱን ሰው ወንጀል በዝርዝር .ምን እንደሰራችሁ ..የእያንዳንዱ ወንጀለኛ ድርሻ ምን እደነበረ፤ በተለይ ፕሮፌሰሩና ባለስልጣኖቹ ላይ አተኩረህ ትተነትናለህ.ያንን በቪዲዬ ይቀረፃል…የራስህንም ወንጀል ሳትረሳ ማለት ነው..ኑዛዜ በለው፡፡››
‹‹ያልከኸውን ማለቴ 20 ሚሊዬን ብር ለበተሰቤ የእውነት እንዲያገኙ ካደረክ ያልከኸውን በደስታ አደረጋለሁ፡››
‹‹ለዛ አትጠራጠር. ቀረፃውን የምታረግው ብሩን እንዳገኙ ካረጋገጥክ ቡኃላ ነው፡፡ግን ከዛ ቡኃላ ደግሞ ሌላ አንድ ነገር ይጠበቅቅሀል፡፡››
‹‹ምንድነው?››
‹‹እኛ በመረጥነው ቦታ ላይ አንተ በመረጥከው መንገድ እራስህን ታጠፋለህ፡፡ ››
‹‹ምን?››
‹‹አዎ .ይሄ እኮ ለአንተ አይነቱ ጭራቅ ትልቅ እድል ነው ….እንደ ወንጀልህ ቢሆን እያንዳንዶን የሰውነትህን ብልት እየተቆረጠ ሞትን እስክትለምን መቃተት ነበረብህ ..እና ግን ያው በአንት ልክ አውሬነት ውስጣችን ስሌለ ምህረት አድርገንልህ ነው እንዲህ አይነት የክብር ሞት አማራጭ የቀረበልህ..እራስህን በራስህ እንድታጠፋ ልንተባበርህ ወስነናል፡፡እንዳልኩህ የመሞቻ ዘዴውን ግድ የለም እራስህ መምረጥ ትችላለህ.ከፈለክ በሽጉጥ ፣ከፈለክ በመርዝ ፣ከፈለክ ደግሞ ተንጠልጥለህ…እኛ የመረጥከውን መሳሪያ ያለምንም ክፍያ እናመቻችልሀለን፤እ ምን ተትላለህ?
‹‹ሌላ ምርጫ የለም..››
‹‹አለ››
‹‹ምን ?››አለ በጉጉትና ፡፡
ኩላሊታቸው ተዘረፈባቸው ያልኩህ 35 ሰዎችን በአንድ አዳራሽ ውስጥ እንዲሰበሰቡ አመቻችና እጅ እግርህን በማሰር መሀከላቸው እንጥልሀለን ፤ከዛ የሚሆነውን ማየት እንችላለን››
‹‹እሺ ፕሮፌሰሩስ እንደእኔ ነው ሚሆነው.እንደእኔ አራሱን እንዲያጠፋ ልታደርጉት ነው?፡፡››
‹‹አይ በፍፅም……እሱ አንተ ያገኘሀውን እድል አያገኝም….በእጆቼ ቀስ በቀስ ነው የምገድለው፡፡ምን አልባት አንድ ወር ሊፈጅብኝ ይችላል.ለማንኛውም ማሰቢያ አንድ ቀን አለህ.ነገ በዚህን ሰዓት ተመልሼ እመጣለሁ..የዛን ጊዜ የመጨረሻ ውሳኔህን ታሳሳቀኛለህ፡››ብሎ በራፉን ዘግቶበት ወጥቶ ሄደ
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
እንደነገርከኝ ከሆነ እስከአሁን የ205 ሰዎች ኩላሊት በጥቂት ገንዘብ እየገዛችሁ አንዳንዱንም በአደጋ ሆስፐታል ከገብና ከሞቱ ሰዎች ሰርቃችሁ ሸጣችሆል፡፡የ52 ሰዎች ልብ ሸጣችኋል፡..ሌላም ብዙ ብዙ የሚዘገንኑ ወንጀሎች››
‹‹አዎ.ብዙ ጊዜ እኮ ያልካቸውን ወንጀሎች መፈፀማችንን ነግሬሀለው››
‹‹ምነው ታዲያ ስትፈፅሙት ያልደከማችሁ አሁን ስታወራው አንገሸገሸህ፤ስማኝ ከጠቀስክልኝ ወንጀሎች ውስጥ ቢያንስ ግማሹ በእናንተ ታፍነው ልባቸውና በመዝረፍ እንዲሞቱና ሰውነታቸው በአሲድ ቀልጦ ለቀብር እንኳን እንዳይበቁ የተደረጉ ናቸወ፡..እና 20ሚሊዬን ሳይሆን 20 ቢሊዬን ብር ቢኖርህና እንኳን አያድንህም››
‹‹ግን የዚህ ሀሳብ ጠንሳሽም ዋናው አድራጊ ፈጣሪ እኮ ፕሮፌሰሩ ነው፡፡የእኔና የሺኪው ድርሻ ትንሽ ነው››በማለት እራሱን ለመከላከል ሚያደርገውን ጥረት ቀጠለበት፡፡
በንግግሩ አብዬት ተንቀጠቀጠ‹‹ግን ምን አይነት ህሊና ቢስ ሰው ነህ?እንዚህን ቃላቶች ከአንደበትህ ስታወጣ ትንሽ አያደናቅፍህም?ስማ እኔ የእድሜዬን ግማሽ ማጅራት መቺ ሆኜ አሳልፌያለሁ ፡፡በዚህ ሂደት በስህተት አንድ ሰው በእጄ ላይ አልፎል እና ከዛን ቀን ጀምሮ ንፅህ እንቅልፍ ተኝቼ አላውቅም… እናንተ ያን ሁሉ ሰው እንዲህ ጨፈጭፋችሁ እንዴት ነው በሰላም መተንፈስ የምትችሉት..ምን አይት አውሬነት ነው በውስጣችሁ ያለው?፡፡አሁን ዝም ብለህ ስማኝ …እኔ እናንተን ለመንግስት አሳልፌ ሰጥቼ በ ፍርድ ቤት እስክትዳኙ መጠበቅ እልችልም፡፡ምን አልባትም የሞት ፍርድም ቢፈረድባችሁ አንኳን አያረካኝም››
‹‹እሸ እንዲሆን የምትፈልገውን ንገረኝ?››
‹‹ኩላሊታቸው ለተዘረፉ 35 ሰዎችን ማግኘት ችለናል.እንሱ አንድ ላይ ሆነው ጠበቃ ገዝተው ሆስፒታላችሁን ከሰዋል፡፡እርግጠኛነኝ ፍርድቤቱ ተገቢውን ካሳ ስለሚበይንላቸው የሚከፈለው ከአንተና ከፕሮፌሰሩ ሼር ተቀንሶ ነው፡፡
‹እንዴ ሼኪውስ…ከዚህ ጉዳይ ከተገኘ አያንዳንዱ ትርፍ ተካፋይ ነበሩ እኮ…››
‹‹ጥሩ .ለጊዜው ግን እሳቸውና ዶዬ እዚህ ወንጀል ውስጥ አይካቱም.. ለአንተ ቤተሰብ የሚሰጠውን ብር ከእሳቸው ነው የምቀበለው….በዛ ላይ ዶክተሯና ጓደኛዬ በእሳቸው እጅ ነው ያሉት..ግን እመነኝ ቀኑ ሲደርስ እራሴው ለሰሩት ወንጀል በደንብ አስከፍላቸዋለው ለዛ ቃል ገባልሀለሁ፡፡አንተ ግን ስለሆስፒታሉ ሼር እርሳው.ምንም አይኖርህም፡፡››
‹‹ቤተሰቦቼ እዚህ ወንጀል ውስጥ የሉበትም.ሚስቴ በጣም ሀይማኖተኛ ና ፈርሀ እግዚያብሄር ያላት ሴት ነች .እና በእኔ ሀጥያት እነሱ መቀጣት የለባቸውም.እንድ ያላቸው መተዳደሪያ ደግሞ ይሄ ሆስፒታል የሚገኝ ገቢ ነው››
‹‹እሱን እኮ አየሁ… ሚስትህንም ልጆችህንም አነጋግሬያቸዋለሁ….ስለአንተ በሚዲያም በሰሙት ነገር ተሳቀውና ተሸማቀው ነው ያሉት…..ብትሞት እራሱ ያን ያህል አያዝኑም…እንዴት አንተን የመሰለ የሰይጣን ታናሽ ወንድም እዛ ቤተሰብ ውስጥ ሊኖር እንደቻላ ማሰብ እንኳን አልቻልኩም፡፡
‹‹አዝናለሁ››
‹‹አይ አንተማ ሀዘኔታ የሚባል ነገር ውስጥህ የለም..ይልቅ አሁን ስማኝ…ለቤተሰብ 20 ሚሊየን ጥሬ በር እንዲደርሰቸው አደርጋለው፡ያንን በስልክ እንድታረጋግጥ ይደረጋል፤ከዛ ቡኃላ ግን ያልከሀውን ታደርጋለህ›
በመጀመሪያ የእያንዳንዱን ሰው ወንጀል በዝርዝር .ምን እንደሰራችሁ ..የእያንዳንዱ ወንጀለኛ ድርሻ ምን እደነበረ፤ በተለይ ፕሮፌሰሩና ባለስልጣኖቹ ላይ አተኩረህ ትተነትናለህ.ያንን በቪዲዬ ይቀረፃል…የራስህንም ወንጀል ሳትረሳ ማለት ነው..ኑዛዜ በለው፡፡››
‹‹ያልከኸውን ማለቴ 20 ሚሊዬን ብር ለበተሰቤ የእውነት እንዲያገኙ ካደረክ ያልከኸውን በደስታ አደረጋለሁ፡››
‹‹ለዛ አትጠራጠር. ቀረፃውን የምታረግው ብሩን እንዳገኙ ካረጋገጥክ ቡኃላ ነው፡፡ግን ከዛ ቡኃላ ደግሞ ሌላ አንድ ነገር ይጠበቅቅሀል፡፡››
‹‹ምንድነው?››
‹‹እኛ በመረጥነው ቦታ ላይ አንተ በመረጥከው መንገድ እራስህን ታጠፋለህ፡፡ ››
‹‹ምን?››
‹‹አዎ .ይሄ እኮ ለአንተ አይነቱ ጭራቅ ትልቅ እድል ነው ….እንደ ወንጀልህ ቢሆን እያንዳንዶን የሰውነትህን ብልት እየተቆረጠ ሞትን እስክትለምን መቃተት ነበረብህ ..እና ግን ያው በአንት ልክ አውሬነት ውስጣችን ስሌለ ምህረት አድርገንልህ ነው እንዲህ አይነት የክብር ሞት አማራጭ የቀረበልህ..እራስህን በራስህ እንድታጠፋ ልንተባበርህ ወስነናል፡፡እንዳልኩህ የመሞቻ ዘዴውን ግድ የለም እራስህ መምረጥ ትችላለህ.ከፈለክ በሽጉጥ ፣ከፈለክ በመርዝ ፣ከፈለክ ደግሞ ተንጠልጥለህ…እኛ የመረጥከውን መሳሪያ ያለምንም ክፍያ እናመቻችልሀለን፤እ ምን ተትላለህ?
‹‹ሌላ ምርጫ የለም..››
‹‹አለ››
‹‹ምን ?››አለ በጉጉትና ፡፡
ኩላሊታቸው ተዘረፈባቸው ያልኩህ 35 ሰዎችን በአንድ አዳራሽ ውስጥ እንዲሰበሰቡ አመቻችና እጅ እግርህን በማሰር መሀከላቸው እንጥልሀለን ፤ከዛ የሚሆነውን ማየት እንችላለን››
‹‹እሺ ፕሮፌሰሩስ እንደእኔ ነው ሚሆነው.እንደእኔ አራሱን እንዲያጠፋ ልታደርጉት ነው?፡፡››
‹‹አይ በፍፅም……እሱ አንተ ያገኘሀውን እድል አያገኝም….በእጆቼ ቀስ በቀስ ነው የምገድለው፡፡ምን አልባት አንድ ወር ሊፈጅብኝ ይችላል.ለማንኛውም ማሰቢያ አንድ ቀን አለህ.ነገ በዚህን ሰዓት ተመልሼ እመጣለሁ..የዛን ጊዜ የመጨረሻ ውሳኔህን ታሳሳቀኛለህ፡››ብሎ በራፉን ዘግቶበት ወጥቶ ሄደ
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍38❤7
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሦስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ሶራ የመጀመሪያ ዲግሪውን ያገኘው በሺ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ ዓመተ ምህረት ነው። ከዚያም በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶችና በረጂ ድርጅቶች ሰርቷል። ሥራ መቀያየሩ ግን ሆዱን እንደ እንቁራሪት ሆድ ከማሳበጥ በስተቀር ያገኘው የሕይወት እርካታ
የለም። የት ቢሄድ ምን
ቢሆን የህሊና እርካታ እንደሚያገኝ
አያውቅም ዩኒቨርስቲ ውስጥ እያለ ኢኮኖሚክስ ዲፓርትመንትን የመረጠው በጓደኞቹ ምክርና ግፊት ነው።
"...አትሞኝ! ጥሩ ደመወዝ ለማግኘት አዲሳባ ለመመደብ ዕድልተህ እንዲሰፋ ከፈለግህ" እያሉ የሰማይ ጥገት የሚመኙ ጓደኞቹ እየነዱ ወደ አልተመኘው ዲፓርትመንት
ሃሳቡን አኮላሽተው
አስገቡት።
ከአደገበት· ቀዬ ከተንቦራቸበት የኤርቦሬ ምድርም ዳግመኛ ሳይመለስ የውሃ ሽታ ሆኖ ወደ መጣበት ተመልሶ መግባት የማይታሰብ ገደል ሆነበት። በልጅነቱ ወደ ዘመናዊ ትምህርት ሊሄድ
ጥብቆ ሲለብስ
ሽማግሌዎችም ሲመርቁት
“…እንደ ጅብ በነጋበት የምትቀር አትሁን። የአያት የቅድመ አያቶችህን ደንብ አክባሪ ለወገንህ ተቆርቋሪ መሆንህን የምታስመሰክር ሁን ብትጠፋ እንኳ የእነሱ ዘር ነው የሚያሰኝህን
ኤርቦሬነትህን አታጥፋ።
ኤርቦሬ ውስጥ ሪስ ፋርቶ ሃልዝጋለች አልሞቅ ሩፍ ህፀንቴ ኤቡሬ ጋሮራ
ጋራንጉዶ ጋርሌ ዲሳ የሚባል ዘር አለ ወደምትሄድበት አገር ስትደርስ የከብት ጆሮ
አበሳሳችሁ እንዴት ነው? ህፃን ልጅ እንደ ተወለደስ መጀመሪያ የምታቀምሱት ምንድን ነው?ብዙ ጊዜ የምትጋቡትስ ከማን
ከማን ጋር ነው?..." ብለህ ጠይቅ።
“...የአንተ ዘር የከብት ጆሮ አበሳስ ታችኛውን የጆሮ ክፍል ከውስጥ ወደ ውጭ በመብሳት ሲሆን! ህፃን ልጅ እንደተወለደ የቡና
ፍሬ ማሽላ የከብት ጥፍር ከህፃኑ ልጅ ሽንት ጋር ተቀላቅሎ ይሰጠዋል። ብዙ ጊዜ ጋብቻ ከቦረናና ፀማይ ጋር ነው። ስለዚህ
ይህን በሄድህበት ሁሉ እየነገርህ ዘርህን ብትጠይቅ ካለጥርጥር
ታገኛቸዋለህ: ከዚያ የቤተስባችሁ አባል ከሌላ አገር ስለመጣ ተቀበሉት ብለው ከዘሮችህ ያደባልቁሃል:
ወደ ሌላ አገር የሄደና የሞተ አንድ ነው እስካልታዩ ድረስ:: ልዩነቱ ያልሞተ ከሄደበት ይመለሳል ! ያኔ ወደ ቤተሰቡ ከመቀላቀሉ በፊት የመንደሩ ሰዎች ማንም ሰው ጠጥቶበት
በማያውቅ ቅል ውሃ ሞልተው ይይዙና ከፊት ለፊቱ ውሃውን እየደፉ መሬቱን በማርጠብ እርጥቡን እግር" ከቤተሰቡ ጋር ይደባልቁታል! ካለበለዚያ ግን ማንም የቤተሰቡ አባል ቢያየውም
ሰላም አይለውም:: እና! አንተም ክሄድክበት ስትመለስ ይኸ ደንብ
እንደሚሰራልህ አትርሳ: ከደንቡ በኋላ ከኤርቦሬ ወንድሞችህ ጋር ጫካ ትወርድና ያገኘኸውን አውሬ ገለህ ስትመጣ ከወላጆችህ በር ፊት ለፊት የእድሜ ጓደኞችህ "ዘውትር ምሽት እየዘፈኑ እያቅራሩ አንዱ የሌላውን ጀርባ ሸፍኖ እየተቀመጠ የአባትህ ቤት የጀግና ቤት መሆኑን እያወደሱ ሲያደምቁት ይሰነብታሉ… ከዚያ ተድረህ ወልደህ ከብደህ ጋንደሩባ ኡላም ሙራል ወይም እጉዴ ትኖራለህ።
“ ኤርቦሬ በአሁኑ ጊዜ ስልጣን የያዘው የኦጌልሻ ሄር ሲሆን ኦጌልሻ ሄር ስልጣነን የተረከበው ከሜልባሳ ሄር ነው።
“በአባትህ ባህል በአርባ ዓመት አንድ ጊዜ አሮጌው ገዥ ሄር በአዲሱ ገዥ ሄር ይተካል:: ይህም ኦቤርሻ ጂም ጊድማ ጂም
ማሮሌ ጂምና ዋተኛ ጂም ሲሆን የመጀመሪያው ጂም ከአስር እስከ አስራ ስምንት ዓመት ዕድሜ ያላቸው ወጣቶች ሲሆኑ ኦቤርሻ ጂም ይባላሉ: ከዚያ ከጨቅላነት እስከ ዘጠኝ ዓመት ያሉት ህፃናት
አድገው ከአስር እስከ አስራ ስምንት አመት ሲሞላቸው ጊድማ ጂም ይሆናሉ። ያም ማለት ከኦቤርሻ ጂም እስከ ጊድማ ጂም ዘጠኝ ዓመት
ይሆናል ቀጥሎ ደግሞ ከጊድማ ጂም በታች ካሉት ጨቅላዎች እስከ ዘጠኝ ዓመት ያሉት አድገው ከአስር አመት እስከ አስራ ስምንት ዓመት ሲሞላቸው ማሮሌ ጂምን ይመሰርታሉ።
ይህም ዘጠኝ ዓመት
ይፈጃል። ከማሮሌ በታች ያሉት ከጨቅላነት እስከ "ዘጠኝ ዓመት ያሉት አድገው ከአስር እስከ አስራ ስምንት ዓመት ሲሞላቸው ደግሞ ዋተኛ ጂም ይባላሉ።
“ስለዚህ ኦቤርሻ ጂም ዘጠኝ ጊዴማ ጅም ዘጠኝ ማርሌና የአራቱን ጂም
ዋተኛ ጂም እያንዳንዳቸው ዘጠኝ ዘጠኝ ስለሚቆዩ
ለመፈፀም ሰላሳ ስድስት አመት የሚፈጅ ሲሆን አሮጌውን የገዥ ሄር
ከተለያዩ እድሜ ከሴትና ወንድ በእኩል የተሰባሰበውን አዲስ ሄር
አጠቃላይ የኤርቦራ ማህበረሰብ በተሰበሰበበት በተለያዩ ባህላዊ ስነስርዓቶች ስልጣን ከአሮጌው ሄር ይረከብና በጋንደሩባ ኩላም
ሙራልና እጉዴ አንዳንድ ከርነት (ጠቅላይ ሚኒስቴር) ይመረጣል። ከርነት ሆኖ የተመረጠው ሰው ካለ ግልድም በስተቀር ልብስ
አይለብስም። ባህሪውም የተመሰገነ ትሁት... መሆን ይገባዋል። ይህ ሰው የአባት ደንብና አሁን ያለው የኤርቦሬ ህዝብ የአደራ ቀንበር የሚጫንበት በሬ ነው: ጎረምሶችም የራሳቸውን የጦርነት ጊዜ
አዝማች 'መሪናኔት' መርጠው የነብር ቆዳ ያለብሱታል: ይህም ሰው
በጦርነት ጊዜ ስልት አውጭና ደረቱን ለጦር ሰጥቶ ለህዝቡ መከታ
የሚሆን ነው።
“ከዚያ የፖለቲካ መሪ የሚሆኑት አራቱ ከርነቶች
ከመንፈሳዊ መሪዎች (ቃውቶች) የአገር ሽማግሌዎች (ጃላቦች) ጋር
ስልጣናቸውን ለሚቀጥለው ወጣት ሄር ያስረክባሉ። ስለዚህ አንተ አሁን በስልጣን ላይ ያለው የኦጌልሻ ሄር አባል በመሆንህ ቶሎ ተመልሰህ
ማህበረሰብህን መርዳትህን አትዘንጋ: እስከዚያው ግን
ወገኖችህ ፀሐይ ወጥታ እስክትገባ ሳንሰለች እንጠብቅሃለን፡፡ ይህ ኸሊናህ ሳይጎድፍ ተመልሰህ ናና ከማህበረሰብህ ተቀላቀል...” ብለውት ነበር።
አካሉ እያደገ ህሊናው እየበሰለ ሲሄድ ግን ከዘመዶቹ አደራ በላይ የአገሩ የአህጉሩ ባጠቃላይ የሰው ልጆችን የመርዳት አደራ ፕላኔቷን የመጠበቅ ግዴታ... እንዳለበት እንኳን ተረድቶ ነበር። በጎ
አስተሳሰቡን ግን ውሃ በላው። አፍንጫው ጥቅም ውስጥ እየተሰነቀረ
ሆዱ ለእለት ደስታ እየተነጠፈ አስቸገረው መቆፈሪያ አንስቶ
የድህነት ተራራ ለመናድ የማንዴላ እናት አምጣ እንድትወልደው ኃይልን እንድታቀብለው ፈለገ እየቆየ ግን አንድ ሃሣብ በህሊናው
ማውጣት ማውረድ ጀመረ።: ቢያንስ በግሉ አንድ ሆዝብን ሊረዳ
ድርጅት መክፈት። ለዚህም ደግሞ ገንዘብ ያሻዋል። ገንዘብ ያላቸው ሰዎች መዳፍ ገብቶ እንደ ቆሎ እያሹ ጉልበቱን ቆረጣጥመው ምስጥ
እንደበላው ግንድ ገንድሰው እንዲጥሉት ግን አልፈለገም
ነፃ መሆንን መረጠ፡
ለዚህ ግን አልታደለም። ያለበት ዘመን ህይወት በገንዘብ የሚተመንበት የገንዘብ ኃይል ነጋሪት እየተጎሰመ በሚለፈፍበት ጊዜ ነው። ዓላማውን ለማሳካት ግን አንድ አማራጭ አለው: ሰርቶ
የማግኛ ስደት: "ስደት ግን ሽሽት ነው" ብሎ ያምን ነበር: ከዚህ ህዝብ ጋር የበላውን በልቶ የጠጣውን ጠጥቶ ከንፈር እየመጠጡ
ማስተዛኑም ደግሞ ድፍረት እንዳልሆነ ተረዳ። ኤርቦሬ አደራ ይዞ ወጣ፤ አልተመለሰም እና! አደራውን በላ: ከአገሩ ሰርቶ
ለማግኘት ብሎ ሄዶ ፍርፋሬ ቢጥመውስ፤ አዲስ ምኞት ህሊናው ቢያረግዝስ እንደገና ክህደት ሊፈፅም? ስለዚህ ለመወሰን ብዙ
አማጠ ከወሰነ በኋላም ህልሙን እውን ለማድረግ ብዙ ጣረ፤ ግን ተሳካለት። እንደ ደረቀ እንጨት የተለዬ ሆነ እንጂ።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሦስት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ሶራ የመጀመሪያ ዲግሪውን ያገኘው በሺ ዘጠኝ መቶ ሰማንያ ዓመተ ምህረት ነው። ከዚያም በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶችና በረጂ ድርጅቶች ሰርቷል። ሥራ መቀያየሩ ግን ሆዱን እንደ እንቁራሪት ሆድ ከማሳበጥ በስተቀር ያገኘው የሕይወት እርካታ
የለም። የት ቢሄድ ምን
ቢሆን የህሊና እርካታ እንደሚያገኝ
አያውቅም ዩኒቨርስቲ ውስጥ እያለ ኢኮኖሚክስ ዲፓርትመንትን የመረጠው በጓደኞቹ ምክርና ግፊት ነው።
"...አትሞኝ! ጥሩ ደመወዝ ለማግኘት አዲሳባ ለመመደብ ዕድልተህ እንዲሰፋ ከፈለግህ" እያሉ የሰማይ ጥገት የሚመኙ ጓደኞቹ እየነዱ ወደ አልተመኘው ዲፓርትመንት
ሃሳቡን አኮላሽተው
አስገቡት።
ከአደገበት· ቀዬ ከተንቦራቸበት የኤርቦሬ ምድርም ዳግመኛ ሳይመለስ የውሃ ሽታ ሆኖ ወደ መጣበት ተመልሶ መግባት የማይታሰብ ገደል ሆነበት። በልጅነቱ ወደ ዘመናዊ ትምህርት ሊሄድ
ጥብቆ ሲለብስ
ሽማግሌዎችም ሲመርቁት
“…እንደ ጅብ በነጋበት የምትቀር አትሁን። የአያት የቅድመ አያቶችህን ደንብ አክባሪ ለወገንህ ተቆርቋሪ መሆንህን የምታስመሰክር ሁን ብትጠፋ እንኳ የእነሱ ዘር ነው የሚያሰኝህን
ኤርቦሬነትህን አታጥፋ።
ኤርቦሬ ውስጥ ሪስ ፋርቶ ሃልዝጋለች አልሞቅ ሩፍ ህፀንቴ ኤቡሬ ጋሮራ
ጋራንጉዶ ጋርሌ ዲሳ የሚባል ዘር አለ ወደምትሄድበት አገር ስትደርስ የከብት ጆሮ
አበሳሳችሁ እንዴት ነው? ህፃን ልጅ እንደ ተወለደስ መጀመሪያ የምታቀምሱት ምንድን ነው?ብዙ ጊዜ የምትጋቡትስ ከማን
ከማን ጋር ነው?..." ብለህ ጠይቅ።
“...የአንተ ዘር የከብት ጆሮ አበሳስ ታችኛውን የጆሮ ክፍል ከውስጥ ወደ ውጭ በመብሳት ሲሆን! ህፃን ልጅ እንደተወለደ የቡና
ፍሬ ማሽላ የከብት ጥፍር ከህፃኑ ልጅ ሽንት ጋር ተቀላቅሎ ይሰጠዋል። ብዙ ጊዜ ጋብቻ ከቦረናና ፀማይ ጋር ነው። ስለዚህ
ይህን በሄድህበት ሁሉ እየነገርህ ዘርህን ብትጠይቅ ካለጥርጥር
ታገኛቸዋለህ: ከዚያ የቤተስባችሁ አባል ከሌላ አገር ስለመጣ ተቀበሉት ብለው ከዘሮችህ ያደባልቁሃል:
ወደ ሌላ አገር የሄደና የሞተ አንድ ነው እስካልታዩ ድረስ:: ልዩነቱ ያልሞተ ከሄደበት ይመለሳል ! ያኔ ወደ ቤተሰቡ ከመቀላቀሉ በፊት የመንደሩ ሰዎች ማንም ሰው ጠጥቶበት
በማያውቅ ቅል ውሃ ሞልተው ይይዙና ከፊት ለፊቱ ውሃውን እየደፉ መሬቱን በማርጠብ እርጥቡን እግር" ከቤተሰቡ ጋር ይደባልቁታል! ካለበለዚያ ግን ማንም የቤተሰቡ አባል ቢያየውም
ሰላም አይለውም:: እና! አንተም ክሄድክበት ስትመለስ ይኸ ደንብ
እንደሚሰራልህ አትርሳ: ከደንቡ በኋላ ከኤርቦሬ ወንድሞችህ ጋር ጫካ ትወርድና ያገኘኸውን አውሬ ገለህ ስትመጣ ከወላጆችህ በር ፊት ለፊት የእድሜ ጓደኞችህ "ዘውትር ምሽት እየዘፈኑ እያቅራሩ አንዱ የሌላውን ጀርባ ሸፍኖ እየተቀመጠ የአባትህ ቤት የጀግና ቤት መሆኑን እያወደሱ ሲያደምቁት ይሰነብታሉ… ከዚያ ተድረህ ወልደህ ከብደህ ጋንደሩባ ኡላም ሙራል ወይም እጉዴ ትኖራለህ።
“ ኤርቦሬ በአሁኑ ጊዜ ስልጣን የያዘው የኦጌልሻ ሄር ሲሆን ኦጌልሻ ሄር ስልጣነን የተረከበው ከሜልባሳ ሄር ነው።
“በአባትህ ባህል በአርባ ዓመት አንድ ጊዜ አሮጌው ገዥ ሄር በአዲሱ ገዥ ሄር ይተካል:: ይህም ኦቤርሻ ጂም ጊድማ ጂም
ማሮሌ ጂምና ዋተኛ ጂም ሲሆን የመጀመሪያው ጂም ከአስር እስከ አስራ ስምንት ዓመት ዕድሜ ያላቸው ወጣቶች ሲሆኑ ኦቤርሻ ጂም ይባላሉ: ከዚያ ከጨቅላነት እስከ ዘጠኝ ዓመት ያሉት ህፃናት
አድገው ከአስር እስከ አስራ ስምንት አመት ሲሞላቸው ጊድማ ጂም ይሆናሉ። ያም ማለት ከኦቤርሻ ጂም እስከ ጊድማ ጂም ዘጠኝ ዓመት
ይሆናል ቀጥሎ ደግሞ ከጊድማ ጂም በታች ካሉት ጨቅላዎች እስከ ዘጠኝ ዓመት ያሉት አድገው ከአስር አመት እስከ አስራ ስምንት ዓመት ሲሞላቸው ማሮሌ ጂምን ይመሰርታሉ።
ይህም ዘጠኝ ዓመት
ይፈጃል። ከማሮሌ በታች ያሉት ከጨቅላነት እስከ "ዘጠኝ ዓመት ያሉት አድገው ከአስር እስከ አስራ ስምንት ዓመት ሲሞላቸው ደግሞ ዋተኛ ጂም ይባላሉ።
“ስለዚህ ኦቤርሻ ጂም ዘጠኝ ጊዴማ ጅም ዘጠኝ ማርሌና የአራቱን ጂም
ዋተኛ ጂም እያንዳንዳቸው ዘጠኝ ዘጠኝ ስለሚቆዩ
ለመፈፀም ሰላሳ ስድስት አመት የሚፈጅ ሲሆን አሮጌውን የገዥ ሄር
ከተለያዩ እድሜ ከሴትና ወንድ በእኩል የተሰባሰበውን አዲስ ሄር
አጠቃላይ የኤርቦራ ማህበረሰብ በተሰበሰበበት በተለያዩ ባህላዊ ስነስርዓቶች ስልጣን ከአሮጌው ሄር ይረከብና በጋንደሩባ ኩላም
ሙራልና እጉዴ አንዳንድ ከርነት (ጠቅላይ ሚኒስቴር) ይመረጣል። ከርነት ሆኖ የተመረጠው ሰው ካለ ግልድም በስተቀር ልብስ
አይለብስም። ባህሪውም የተመሰገነ ትሁት... መሆን ይገባዋል። ይህ ሰው የአባት ደንብና አሁን ያለው የኤርቦሬ ህዝብ የአደራ ቀንበር የሚጫንበት በሬ ነው: ጎረምሶችም የራሳቸውን የጦርነት ጊዜ
አዝማች 'መሪናኔት' መርጠው የነብር ቆዳ ያለብሱታል: ይህም ሰው
በጦርነት ጊዜ ስልት አውጭና ደረቱን ለጦር ሰጥቶ ለህዝቡ መከታ
የሚሆን ነው።
“ከዚያ የፖለቲካ መሪ የሚሆኑት አራቱ ከርነቶች
ከመንፈሳዊ መሪዎች (ቃውቶች) የአገር ሽማግሌዎች (ጃላቦች) ጋር
ስልጣናቸውን ለሚቀጥለው ወጣት ሄር ያስረክባሉ። ስለዚህ አንተ አሁን በስልጣን ላይ ያለው የኦጌልሻ ሄር አባል በመሆንህ ቶሎ ተመልሰህ
ማህበረሰብህን መርዳትህን አትዘንጋ: እስከዚያው ግን
ወገኖችህ ፀሐይ ወጥታ እስክትገባ ሳንሰለች እንጠብቅሃለን፡፡ ይህ ኸሊናህ ሳይጎድፍ ተመልሰህ ናና ከማህበረሰብህ ተቀላቀል...” ብለውት ነበር።
አካሉ እያደገ ህሊናው እየበሰለ ሲሄድ ግን ከዘመዶቹ አደራ በላይ የአገሩ የአህጉሩ ባጠቃላይ የሰው ልጆችን የመርዳት አደራ ፕላኔቷን የመጠበቅ ግዴታ... እንዳለበት እንኳን ተረድቶ ነበር። በጎ
አስተሳሰቡን ግን ውሃ በላው። አፍንጫው ጥቅም ውስጥ እየተሰነቀረ
ሆዱ ለእለት ደስታ እየተነጠፈ አስቸገረው መቆፈሪያ አንስቶ
የድህነት ተራራ ለመናድ የማንዴላ እናት አምጣ እንድትወልደው ኃይልን እንድታቀብለው ፈለገ እየቆየ ግን አንድ ሃሣብ በህሊናው
ማውጣት ማውረድ ጀመረ።: ቢያንስ በግሉ አንድ ሆዝብን ሊረዳ
ድርጅት መክፈት። ለዚህም ደግሞ ገንዘብ ያሻዋል። ገንዘብ ያላቸው ሰዎች መዳፍ ገብቶ እንደ ቆሎ እያሹ ጉልበቱን ቆረጣጥመው ምስጥ
እንደበላው ግንድ ገንድሰው እንዲጥሉት ግን አልፈለገም
ነፃ መሆንን መረጠ፡
ለዚህ ግን አልታደለም። ያለበት ዘመን ህይወት በገንዘብ የሚተመንበት የገንዘብ ኃይል ነጋሪት እየተጎሰመ በሚለፈፍበት ጊዜ ነው። ዓላማውን ለማሳካት ግን አንድ አማራጭ አለው: ሰርቶ
የማግኛ ስደት: "ስደት ግን ሽሽት ነው" ብሎ ያምን ነበር: ከዚህ ህዝብ ጋር የበላውን በልቶ የጠጣውን ጠጥቶ ከንፈር እየመጠጡ
ማስተዛኑም ደግሞ ድፍረት እንዳልሆነ ተረዳ። ኤርቦሬ አደራ ይዞ ወጣ፤ አልተመለሰም እና! አደራውን በላ: ከአገሩ ሰርቶ
ለማግኘት ብሎ ሄዶ ፍርፋሬ ቢጥመውስ፤ አዲስ ምኞት ህሊናው ቢያረግዝስ እንደገና ክህደት ሊፈፅም? ስለዚህ ለመወሰን ብዙ
አማጠ ከወሰነ በኋላም ህልሙን እውን ለማድረግ ብዙ ጣረ፤ ግን ተሳካለት። እንደ ደረቀ እንጨት የተለዬ ሆነ እንጂ።
👍21
“ኤርቦሬ" የሚለውን ስያሜ ያወጡት ሐመሮች ናቸው።
በሐመርኛ ቋንቋ “ኤር' ማለት ህዝብ “ቦሬ" ደግሞ ቦረና ማለት ነው።
ኤር ቦሬ' በቋንቋው ጥቅል ትርጉም “ከቦረና የመጣ ህዝብ" ማለት ነው
ኤርቦሬዎች ከኤሎ የተራራ ሰንሰለት በስተ ምስራቅ ከቦረና በስተምዕራብ በደቡብ ምስራቅ ከሐመር በደቡብ ከኬንያ ድንበር
ተዋስነው በረባዳማው የወይጦ ሜዳ የሚኖሩ ህዝቦች ናቸው:
በጆግራፊያዊ አቀማመጡ ሰበብ ማህበረሰቡ ለሁለት የተከፈለ ሲሆን በስተሰሜን ያለው ኤርቦሮ በጋንዱሩባና ኩሳም፤ ማርሌ በመባል በሙራልና በእጉዴ መንደር የሚኖሩ ናቸው።
በአርባ አመት አንዴ በሚደረገው የስልጣን ሽግግር አጠቃላይ የማህበረሰቡ አባል ሴት ወንድ ህፃን ሳይል በየቤቱ
ውስጥ የነበረውን እሳት አጥፍቶ ይወጣና በአንድ ላይ ይሰባሰባል፤
አዲስ እሳት በሰበቃ ይቀጣጠላል ፤ ከብት ይታረዳል። ጎረምሶችና
ጎልማሶችም በሰልፍ ሆነው የከብቱን ደም በጣታቸው ግንባራቸው ላይ እየቀቡ ወደ ህዝቡ እንዲቀላቀሉ ይደረጋል ቃል ኪዳን ነው::
በኤርቦሬ ባህል ልጃገረድን ካለፈቃዷ የደፈረ የተወገዘ
በመሆኑ ከወንዶች መካከል ይህን የፈፀመ ወንጀለኛ ካለ በጣቱ የከብቱን ደም ነክቶ ግንባሩን አይቀባም ጓደኛው ደም ነክቶ ፊቱን ሳይዞር ጣቱ ላይ ይቀባለታል ማህበረሰቡ በጥላቻ ያየዋል ቃል ኪዳን አፍራሹን ድርጊቱም በሁሉም ይወገዛል። ደንብ ጣሹም በመጥፎ ተግባሩ ተደናግጦ እንደ ተቆረጠ ቅጠል ሲጠወልግ ሲወይብ ይታያል። ማህበረሰቡ እውነት በእጁ ነች: የዋሸ የደበቀ ያታለለ የሰውነቱ ቆዳ እስኪገለበጥ እየተገረፈ አይቀጡ ቅጣት
ይቀጣል። ጥፋቱን ካመነና ሲሸማቀቅ ከታዬ ግን ከህሊና ቅጣት በላይ ቅጣት አይሰጠውም: የማህበረሰቡ የዝምታ ሳማ ህሊናውን የለበለበው ግን ሁለተኛ ጥፋቱን አይደግምም።
በበዓሉ ይበላል ይጠጣል ይጨፈራል። ከዚያ አሮጌው
የገዥ ሄር ስልጣኑን ለአዲሱ ገዥ ሄር ትውልድ በሰላም ያዙኝ ልቀቁኝ ሳይል ያስረክባል። አዲሱ ገዥ ሄርም የራሱን ጠቅላይ
እና ሽማግሌዎች ይመርጥና ሚኒስተሮች የጦር መሪዎች
ከሃይማኖታዊ ንጉሶች ጋር ተባብረው ለመስራት ቃል ኪዳን ይገባሉ፡
ይህ ትውልድ ካለፈው ትውልድ የተቀበለውን ኃላፊነት እስኪወጣ
ከፀሐይ መውጫ ወደ ፀሐይ መግቢያ በረድፍ ጎጆ ቤት የሚሰራ ሲሆን በእድሜ በጣም አነስተኛው በፀሐይ መውጫ በኩል ይሆንና እንደ ዕድሜው ደረጃ ከምስራቅ ወደ ምዕራብ ይደረደሩና ከመሪው ትውልድ በእድሜ ከፍተኛው በፀሐይ መግቢያው ያለው ጎጆ ይገባል።
ይህም ወጣቱ ለማህበረሰቡ ለረጅም ጊዜ ማገልገል የመቻሉን ተስፋና ሃላፊነቱን የመግለጫ ዘዴ ሲሆን ሽማግሌም
የህይወት ጮራው እስክትጠልቅበት ድረስ ማህበረሰቡን ባለው አቅም
አገልግሉ ማለፍ እንዳለበትና ፊትና ኋላ ሆኖ ማለፍ የማይቀር የማይፈሩት የተፈጥሮ ክስተት መሆኑን እየተረዳ ከሞቱ በፊት ቀና
ተግባራትን የመፈፀሙን አርአያነት የሚያሳይ ነው።
ስለዚህ የእድሜ ባለፀጋው የበኩሉን እየፈፀመ ሲሞት ሌላው እየተሸጋሸገ የዚያ ትውልድ የገዥነት ዘመን ሲደርስ አዲስ ምርጫ
ይደረጋል: ያኔ አሮጌው እሳት ይጠፋል። አዲስ እሳት ለማህበረሰቡ
ይለኮሳል... አዲሱ ትውልድም የራሱን ትውልድ መሪዎች መርጦ
ማህበረሰቡን ያገለግላል።
💫ይቀጥላል💫
በሐመርኛ ቋንቋ “ኤር' ማለት ህዝብ “ቦሬ" ደግሞ ቦረና ማለት ነው።
ኤር ቦሬ' በቋንቋው ጥቅል ትርጉም “ከቦረና የመጣ ህዝብ" ማለት ነው
ኤርቦሬዎች ከኤሎ የተራራ ሰንሰለት በስተ ምስራቅ ከቦረና በስተምዕራብ በደቡብ ምስራቅ ከሐመር በደቡብ ከኬንያ ድንበር
ተዋስነው በረባዳማው የወይጦ ሜዳ የሚኖሩ ህዝቦች ናቸው:
በጆግራፊያዊ አቀማመጡ ሰበብ ማህበረሰቡ ለሁለት የተከፈለ ሲሆን በስተሰሜን ያለው ኤርቦሮ በጋንዱሩባና ኩሳም፤ ማርሌ በመባል በሙራልና በእጉዴ መንደር የሚኖሩ ናቸው።
በአርባ አመት አንዴ በሚደረገው የስልጣን ሽግግር አጠቃላይ የማህበረሰቡ አባል ሴት ወንድ ህፃን ሳይል በየቤቱ
ውስጥ የነበረውን እሳት አጥፍቶ ይወጣና በአንድ ላይ ይሰባሰባል፤
አዲስ እሳት በሰበቃ ይቀጣጠላል ፤ ከብት ይታረዳል። ጎረምሶችና
ጎልማሶችም በሰልፍ ሆነው የከብቱን ደም በጣታቸው ግንባራቸው ላይ እየቀቡ ወደ ህዝቡ እንዲቀላቀሉ ይደረጋል ቃል ኪዳን ነው::
በኤርቦሬ ባህል ልጃገረድን ካለፈቃዷ የደፈረ የተወገዘ
በመሆኑ ከወንዶች መካከል ይህን የፈፀመ ወንጀለኛ ካለ በጣቱ የከብቱን ደም ነክቶ ግንባሩን አይቀባም ጓደኛው ደም ነክቶ ፊቱን ሳይዞር ጣቱ ላይ ይቀባለታል ማህበረሰቡ በጥላቻ ያየዋል ቃል ኪዳን አፍራሹን ድርጊቱም በሁሉም ይወገዛል። ደንብ ጣሹም በመጥፎ ተግባሩ ተደናግጦ እንደ ተቆረጠ ቅጠል ሲጠወልግ ሲወይብ ይታያል። ማህበረሰቡ እውነት በእጁ ነች: የዋሸ የደበቀ ያታለለ የሰውነቱ ቆዳ እስኪገለበጥ እየተገረፈ አይቀጡ ቅጣት
ይቀጣል። ጥፋቱን ካመነና ሲሸማቀቅ ከታዬ ግን ከህሊና ቅጣት በላይ ቅጣት አይሰጠውም: የማህበረሰቡ የዝምታ ሳማ ህሊናውን የለበለበው ግን ሁለተኛ ጥፋቱን አይደግምም።
በበዓሉ ይበላል ይጠጣል ይጨፈራል። ከዚያ አሮጌው
የገዥ ሄር ስልጣኑን ለአዲሱ ገዥ ሄር ትውልድ በሰላም ያዙኝ ልቀቁኝ ሳይል ያስረክባል። አዲሱ ገዥ ሄርም የራሱን ጠቅላይ
እና ሽማግሌዎች ይመርጥና ሚኒስተሮች የጦር መሪዎች
ከሃይማኖታዊ ንጉሶች ጋር ተባብረው ለመስራት ቃል ኪዳን ይገባሉ፡
ይህ ትውልድ ካለፈው ትውልድ የተቀበለውን ኃላፊነት እስኪወጣ
ከፀሐይ መውጫ ወደ ፀሐይ መግቢያ በረድፍ ጎጆ ቤት የሚሰራ ሲሆን በእድሜ በጣም አነስተኛው በፀሐይ መውጫ በኩል ይሆንና እንደ ዕድሜው ደረጃ ከምስራቅ ወደ ምዕራብ ይደረደሩና ከመሪው ትውልድ በእድሜ ከፍተኛው በፀሐይ መግቢያው ያለው ጎጆ ይገባል።
ይህም ወጣቱ ለማህበረሰቡ ለረጅም ጊዜ ማገልገል የመቻሉን ተስፋና ሃላፊነቱን የመግለጫ ዘዴ ሲሆን ሽማግሌም
የህይወት ጮራው እስክትጠልቅበት ድረስ ማህበረሰቡን ባለው አቅም
አገልግሉ ማለፍ እንዳለበትና ፊትና ኋላ ሆኖ ማለፍ የማይቀር የማይፈሩት የተፈጥሮ ክስተት መሆኑን እየተረዳ ከሞቱ በፊት ቀና
ተግባራትን የመፈፀሙን አርአያነት የሚያሳይ ነው።
ስለዚህ የእድሜ ባለፀጋው የበኩሉን እየፈፀመ ሲሞት ሌላው እየተሸጋሸገ የዚያ ትውልድ የገዥነት ዘመን ሲደርስ አዲስ ምርጫ
ይደረጋል: ያኔ አሮጌው እሳት ይጠፋል። አዲስ እሳት ለማህበረሰቡ
ይለኮሳል... አዲሱ ትውልድም የራሱን ትውልድ መሪዎች መርጦ
ማህበረሰቡን ያገለግላል።
💫ይቀጥላል💫
👍34
የተሰባበሩ ነፍሶች
ምዕራፍ-18
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
//
አቢዬት ከጓደኞቹ ጋር ሆኖ እቤቱን የድግስ ቤት አስመስሎትል።ያልተገዛ መጠጥና ያልተሰናዳ የምግብ አይነት የለም።ይሄ ሁሉ ስርጉድ ዶ/ር ሰጲራን ለመቀበል ነው።አዎ ዛሬ ማታ ከሼክ ጠኸ ሰዎች እጅ ይረከባታል።በህይወቱ በዚህ መጠን ሰው ናፍቆት አያውቅም፡፡ ከፍቅረኛው ጋር ያለው ቀጠሮ እስኪደርስ አላስችል እንዳለው አዲስ አፍቃሪ አስሬ ሞባይሉን እያወጣ ሰዓቱን ያያል።ካሳ ከ10 ሰዓት በፊት የተለቀቀው ።እንደዛ የሆነበት ምክንያት የአቶ ሙሉን የመጨረሻና ወሳኝ ውሳኔ እንዲቀርፅ ከሼክ ጠሀ ጋር በተደረገ ስምምነት ነው።አብዬት ካሳን ሲረከብ አብሮ ሀያ ሚሊዬን ብር ተቀብሎ ለአቶ ሙሉ ቤተሠብ ሚስጥሩ በተጠበቀ ሁኔታ አስረክቦ አቶ ሙሉ እንድያረጋግጥ ከባለቤቱ ጋር በስልክ አገናኝቶት ነበር።
በወቅቱ የባለቤቱ ስሜት ቅስም ሰባሪ ነበር
"ሙሉ አሁን ለእኛ ገንዘብ ምን ያረግልናል ...የሀገር ሁሉ ብር ብትልክልን እኮ ከደረሰብን ውርደት አያወጣንም...ሙሉ ስለአንተ ከሰማሁ በኃላ ቤተክርስቲያን ሄጄ አላውቅም ፡፡ለምን እንደሆነ ታውቃለህ? እግዜር ፊት መቅረብ አፈርኩ...ስለባሌ ቢጠይቀኝ ምን ብዬ መልስለታለሁ...?እኚንና መሠል ስሜት የሚያደፈርሱ ንግግሮችን ከማያባራ እንባ አጅባ ተናገረች፡፡
ከዛ ብኃላ አቶ ሙሉ በስምምነታቸው መሠረት እራሱ የሠራውን...የኘሮፌሰሩን..እና የባለስልጣኖችን... እያንዳንድ የፈፀሙትን የወንጀል አይነትና ያገኙትን ብር በመዘርዘር እና ለእያንዳንድም ያለውን ማስረጃ በማቅረብ ተቀረፀ...ከአብዬት ጋር በገባው ውል መሠረት የሼኪውንና የዶዬን ስም አላነሳም።ግን የአቶ ሙሉን የቪዲዬ ኑዛዜና መረጃ ካየ ብኃላ ፓሊስ ምርመራ መጀመሩና ወደእነዶዬ መቅረብ ስለማይቀር..ከአሁኑ ከውስጣቸው ሁለቱ እራሳቸውን ለፓሊስ አሳልፈው በመስጠት በፕሮፌሰሩ የሚታዘዙትን ወንጀሎች ሁሉ እነሱ ብቻ እንደፈፀሙ እንዲናዘዙ ተመቻችቶል።ያው ልጆቹ የእውነትም በእያንዳንድ ወንጀል ስለነበሩበት የሚሰጡት ቃል ከአቶ ሙሉ ቪዲዬ ጋር እንደማይጣረዝ ታምኖል....ከዛ ከሁለት ወይም ከሶስት ቀን ብኃላ ዶክተር ሰጲራ ከፕሮፌሰሩ እጅ እንዳመለጠች ተደርጎ ከጠበቃዋ ጋር ሆና እጆን ትሰጣለች...በተቻለ መጠን መረጃዎች ሁሉ የእሷን ነፃ መሆን ሲለሚረጋገጥ እስር ቤት ሳታድር በዋስ እንድትለቀቅ የተቻለውን ለማድረግ ውሳኔ ላይ ደርሷ ስለዝርዝር ጉዳዩ ከህግ ሰዎች ጋር ከአሁኑ እየተነጋገሩበት ነው።
አብዬት ከካሳ ጋር ዶክተር ሰጲራን ለመቀበል የተቀጠሩበት ቦታ ደርሰው መኪናቸው አቁመው ገቢና ውስጥ ቁጭ ብለው እስኪያመጡላቸው እየጠበቁ ነው።
አቢዬተት"ግን አሞት ነበር ብለኸኝ ነበር አይደል?"በሰላም አላገኛት ይሆን እንዴ የሚል ጥርጣሬ ውስጡን ስላመሠው ካሳን ጠየቀው።
"ካሳ "አይ አሞታል አላልኩህም ግን ፌንት በልታ ነበር "
"ሰው ሳይታመም ፌንት ይበላል እንዴ"
"አዎ በደስታም ሊያረገው ይችላል"
"ግን ሀኪም አላያትም?"
"አንድ ሀኪም መጥቶ አይቶት ሆስፒታል ሄዳ ተጨማሪ ምርመራ ታድርግ ብሎ ኪኒና ሰጥቷት ሄደ...ግን አሁን ስለእሱ እርሳና አሁን ስትመጣ ቀድሞ አቅፎ የሚስማት ማን ነው?"
"ምን ማለት ነው ከማና ከማ?››
"ከእኔና ከአንተ ነዋ?"
"አንተ ደግሞ ለምንድነው የምታቅፋት"
"እንደ አንተ ሰለማፈቅራት ነዋ"
"አይ አንተ ከስሯ የመጣሀው ዛሬ ነው.. ከእኔ ግን ከ5 አስጨናቂና እረፍት የለሽ ቀናት ብኃላ ነው የማገኛት እና የማቅፍትም የምስማትም እኔው ነኝ"አለው ፡፡ምንም እንኳን ንግግሩ ለካሳ ግራ አጋቢ ንግግር የቀልድ መልስ መስጠት ይምሰል እንጂ በእውነትም ማድረግ የሚፈልገውን ትክክለኛ ስሜቱን ነው ያንፀባረቀው
"ንግግሩን እንዳገባደደ አንድ ማርቼዲስ መኪና እየከነፈች መጣችና አጠገባቸው ቆመች ።አብዬት ሽጉጡን በቀኝ እጅ ያዘና ፈጠን ብሎ ገቢናውን ለቆ ወረደ...የመኪናዋ ገቢና ተከፈተ ዳክተሯን አወረዶትና መኪናዋ ተስፈንጥራ ከአካባቢው ተሠወረች ።አብዬት ሽጉጡን ጎኑ ሻጠና ተንደርድሮ ወደእሷ ሮጠ..እንደደረሰ ሙሉ በሙሉ እጆቹን በወገቦ ዙሪያ ጠመጠመና በአየር ላይ አንስቶ አሽከረከራት።እንደተሸከማት ወደመኪናው ይዛት ሄደ..
"አረ አውርደኝ እከብድሀለው"
"አረ በጣም ቀላል ነሽ...ምግብ አይሰጡሽም ነበር እንዴ?"
"አይ ምግብ ነው ሚያወፍረው ብለህ ነው"
መኪናው ጋር ሲደርስ አወረዳት..ካሳ ገቢና እንደተቀመጠ ነው...አልተንቀሳቀሰም።ስታየው ደነገጠች"
"እንዴ ካሳ መጥተሀል እንዴ"
"መምጣት እንኳን መጥቼ ነበር…ይሄ አውሬ እንዳትወርድ..እንዳትስማት ብሎ አስፈራራኝ እንጂ"አለ በቅሬታ
‹‹ማሙሽ ገቢናውን ልቀቅላትና ከኃላ ግባ አለው ››አብዬት ጣልቃ ገብቶ አዘዘው።
አረ ተወው እኃላ ሆናለው ብላ ከፍታ ገባች..አቢዬትም ገባና መኪናዋን አንቀሳቀሰ
"አብዬት በእስፓኪዬ ወደኃላ አየተመለከታት ነው።ከስታለች..መክሳት ብቻ ሳይሆን ገርጥታለች አይኖቾ ጉድጉድ ከማለታቸው በላይ ቁዝዝ ብለዋል...ለቀናት የረባ እንቅልፍ እንዳልተኛች ያስታውቃል...የጤናዋም ሁኔታ አሳስቦታል።
"እንዴ ወደቤት አይደለ እንዴ የምንሄደው ?ነው ወይስ አድራሻ ቀየራችሁ?"ስትል ጠየቀች።የዚህ ጥያቄ መነሻ አብዬት መኪናዋን እየነዳበት ያለው አቅጣጫ ከቤታቸው አቅጣጫ ጋር ስላልገጠመላት ነው።
"አይ እዛው ነን...እግረ መንገዳችንን እዚህ ሰፈር ጉዳይ ቢጤ ስላለችኝ ነው።አያቆየንም።"
"ጉዳይ ካለህ ታዲያ እኛ ምን አገባን ..አውርደን እና በታክሲ እንሄዳለን"አለ ካሳ ተበሳጭቶ
ዶ/ሯ ደነገጠችና "አረ ችግር የለም..እቤትስ ሄደን ምን እንሰራለን ..እንደውም በዚህ ምሽት ነፍሻማ አየር ከተማውን መዞር አስደሳች ነው...በዛ ላይ አንድ ክፍል ውስጥ ታፍኜ መሠንበቴን አትርሳ"
"ላንቺው ብዬ ነው"
"ለእሷ ብለህ ምን...?"
"ይሄንን ያንተን አስቀያሚ ፊት ለረጂም ሰዓት እያየች እንዳትፈራ ብዬ ነው...ይሄንን ፊት ይዘህ ስታፈቅራት ግን ትንሽ አታሳዝንህም?"
በካሳ ሰቅጣጭ ንግግር ዶክተሯ የምትገባበት ጠፋት.. የአብዬትን ንዴት ለማየት አይኖቾን በፈራ ተባ ወደእሱ ስትልካቸውእሱ በካሳ ንግግር እየሳቀ ነው..መኪናውን አቆመ ፡፡
"ሆስፒታል ደግሞ ምን እንሰራለን?"አሁንን በንጭንጭ ቃና ጥያቄውን የሰነዘረው ካሳ ነው
"አስቀያሚ ፊቴን እንዲያስተካክሉልኝ"
ከእግሩ ስር የነበረ ጥቁር ፔስታል አነሳና ለዶክተር ወደኃላ አቀበላት
"ምንድነው...?››
‹‹ወደ ውስጥ አብረን ስለምንገባ እራስሺን ቀይሪ››
ፔስታሉን ውስጥ ያሉ ቁሳቁሶችን ጎኗ ካለ ወንበር ላይ ዘረገፈችና በየተራ አየቻቸው።
"አንተ እነዚ ዕቃዎች አሁንም አሉ?"
"ከዚህ መከራ ሙሉ በሙሉ እስክንወጣ ያስፈልጉናል ብዬ አስቀምጬቸው ነበር ይሄው ዛሬ አስፈለጉን..››እቃዎቹን
ስታይ ከገዳዬቾ ሽሽት እንዴት እሱ እጅ እንደገባቸ እነዚህን እራስን መቀየሪያ የገዛላት ጊዜ ተሠምቶት የነበረው ስሜት ሁሉም ፊቷ ላይ ድቅን አለ..ፀጉሩን አጠለቀች...መነፅሯን ሰካች...በአንገቷ ዙሪያ ሻርፗን ጠመጠመችና አጠናቀቀች
አቢዬትም ከገቢናውን ለቆ ወረደና የዶ/ሯን በራፍ ከፈተ
‹‹ውረጂ ዶክተር››
ወረደች..
ካሳ "እኔም ልምጣ እንዴ..?"
"ቦሮጫህን ቀደው እንዲያስወግድልህ ከፈለክ ና"
"አይ እንደውም ትቼዋለው.. የመድሀኒት ሽታ በጣም ነው የሚያስጠላኝ።
ትተውት ጎን ለጎን ሆነው ወደውስጥ መጓዝ ጀመሩ
"ለምንድነው ግን ወደእዚህ የመጣነው?"ጠየቀችው
"ታመሽና እራስሽን ስተሽ እንደነበር ሰምቼያለው ምክንያቱን ማወቅ አለብን።››
"እና ነገ ተነገ ወዲያ አይደርስም ነበር?"
ምዕራፍ-18
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
//
አቢዬት ከጓደኞቹ ጋር ሆኖ እቤቱን የድግስ ቤት አስመስሎትል።ያልተገዛ መጠጥና ያልተሰናዳ የምግብ አይነት የለም።ይሄ ሁሉ ስርጉድ ዶ/ር ሰጲራን ለመቀበል ነው።አዎ ዛሬ ማታ ከሼክ ጠኸ ሰዎች እጅ ይረከባታል።በህይወቱ በዚህ መጠን ሰው ናፍቆት አያውቅም፡፡ ከፍቅረኛው ጋር ያለው ቀጠሮ እስኪደርስ አላስችል እንዳለው አዲስ አፍቃሪ አስሬ ሞባይሉን እያወጣ ሰዓቱን ያያል።ካሳ ከ10 ሰዓት በፊት የተለቀቀው ።እንደዛ የሆነበት ምክንያት የአቶ ሙሉን የመጨረሻና ወሳኝ ውሳኔ እንዲቀርፅ ከሼክ ጠሀ ጋር በተደረገ ስምምነት ነው።አብዬት ካሳን ሲረከብ አብሮ ሀያ ሚሊዬን ብር ተቀብሎ ለአቶ ሙሉ ቤተሠብ ሚስጥሩ በተጠበቀ ሁኔታ አስረክቦ አቶ ሙሉ እንድያረጋግጥ ከባለቤቱ ጋር በስልክ አገናኝቶት ነበር።
በወቅቱ የባለቤቱ ስሜት ቅስም ሰባሪ ነበር
"ሙሉ አሁን ለእኛ ገንዘብ ምን ያረግልናል ...የሀገር ሁሉ ብር ብትልክልን እኮ ከደረሰብን ውርደት አያወጣንም...ሙሉ ስለአንተ ከሰማሁ በኃላ ቤተክርስቲያን ሄጄ አላውቅም ፡፡ለምን እንደሆነ ታውቃለህ? እግዜር ፊት መቅረብ አፈርኩ...ስለባሌ ቢጠይቀኝ ምን ብዬ መልስለታለሁ...?እኚንና መሠል ስሜት የሚያደፈርሱ ንግግሮችን ከማያባራ እንባ አጅባ ተናገረች፡፡
ከዛ ብኃላ አቶ ሙሉ በስምምነታቸው መሠረት እራሱ የሠራውን...የኘሮፌሰሩን..እና የባለስልጣኖችን... እያንዳንድ የፈፀሙትን የወንጀል አይነትና ያገኙትን ብር በመዘርዘር እና ለእያንዳንድም ያለውን ማስረጃ በማቅረብ ተቀረፀ...ከአብዬት ጋር በገባው ውል መሠረት የሼኪውንና የዶዬን ስም አላነሳም።ግን የአቶ ሙሉን የቪዲዬ ኑዛዜና መረጃ ካየ ብኃላ ፓሊስ ምርመራ መጀመሩና ወደእነዶዬ መቅረብ ስለማይቀር..ከአሁኑ ከውስጣቸው ሁለቱ እራሳቸውን ለፓሊስ አሳልፈው በመስጠት በፕሮፌሰሩ የሚታዘዙትን ወንጀሎች ሁሉ እነሱ ብቻ እንደፈፀሙ እንዲናዘዙ ተመቻችቶል።ያው ልጆቹ የእውነትም በእያንዳንድ ወንጀል ስለነበሩበት የሚሰጡት ቃል ከአቶ ሙሉ ቪዲዬ ጋር እንደማይጣረዝ ታምኖል....ከዛ ከሁለት ወይም ከሶስት ቀን ብኃላ ዶክተር ሰጲራ ከፕሮፌሰሩ እጅ እንዳመለጠች ተደርጎ ከጠበቃዋ ጋር ሆና እጆን ትሰጣለች...በተቻለ መጠን መረጃዎች ሁሉ የእሷን ነፃ መሆን ሲለሚረጋገጥ እስር ቤት ሳታድር በዋስ እንድትለቀቅ የተቻለውን ለማድረግ ውሳኔ ላይ ደርሷ ስለዝርዝር ጉዳዩ ከህግ ሰዎች ጋር ከአሁኑ እየተነጋገሩበት ነው።
አብዬት ከካሳ ጋር ዶክተር ሰጲራን ለመቀበል የተቀጠሩበት ቦታ ደርሰው መኪናቸው አቁመው ገቢና ውስጥ ቁጭ ብለው እስኪያመጡላቸው እየጠበቁ ነው።
አቢዬተት"ግን አሞት ነበር ብለኸኝ ነበር አይደል?"በሰላም አላገኛት ይሆን እንዴ የሚል ጥርጣሬ ውስጡን ስላመሠው ካሳን ጠየቀው።
"ካሳ "አይ አሞታል አላልኩህም ግን ፌንት በልታ ነበር "
"ሰው ሳይታመም ፌንት ይበላል እንዴ"
"አዎ በደስታም ሊያረገው ይችላል"
"ግን ሀኪም አላያትም?"
"አንድ ሀኪም መጥቶ አይቶት ሆስፒታል ሄዳ ተጨማሪ ምርመራ ታድርግ ብሎ ኪኒና ሰጥቷት ሄደ...ግን አሁን ስለእሱ እርሳና አሁን ስትመጣ ቀድሞ አቅፎ የሚስማት ማን ነው?"
"ምን ማለት ነው ከማና ከማ?››
"ከእኔና ከአንተ ነዋ?"
"አንተ ደግሞ ለምንድነው የምታቅፋት"
"እንደ አንተ ሰለማፈቅራት ነዋ"
"አይ አንተ ከስሯ የመጣሀው ዛሬ ነው.. ከእኔ ግን ከ5 አስጨናቂና እረፍት የለሽ ቀናት ብኃላ ነው የማገኛት እና የማቅፍትም የምስማትም እኔው ነኝ"አለው ፡፡ምንም እንኳን ንግግሩ ለካሳ ግራ አጋቢ ንግግር የቀልድ መልስ መስጠት ይምሰል እንጂ በእውነትም ማድረግ የሚፈልገውን ትክክለኛ ስሜቱን ነው ያንፀባረቀው
"ንግግሩን እንዳገባደደ አንድ ማርቼዲስ መኪና እየከነፈች መጣችና አጠገባቸው ቆመች ።አብዬት ሽጉጡን በቀኝ እጅ ያዘና ፈጠን ብሎ ገቢናውን ለቆ ወረደ...የመኪናዋ ገቢና ተከፈተ ዳክተሯን አወረዶትና መኪናዋ ተስፈንጥራ ከአካባቢው ተሠወረች ።አብዬት ሽጉጡን ጎኑ ሻጠና ተንደርድሮ ወደእሷ ሮጠ..እንደደረሰ ሙሉ በሙሉ እጆቹን በወገቦ ዙሪያ ጠመጠመና በአየር ላይ አንስቶ አሽከረከራት።እንደተሸከማት ወደመኪናው ይዛት ሄደ..
"አረ አውርደኝ እከብድሀለው"
"አረ በጣም ቀላል ነሽ...ምግብ አይሰጡሽም ነበር እንዴ?"
"አይ ምግብ ነው ሚያወፍረው ብለህ ነው"
መኪናው ጋር ሲደርስ አወረዳት..ካሳ ገቢና እንደተቀመጠ ነው...አልተንቀሳቀሰም።ስታየው ደነገጠች"
"እንዴ ካሳ መጥተሀል እንዴ"
"መምጣት እንኳን መጥቼ ነበር…ይሄ አውሬ እንዳትወርድ..እንዳትስማት ብሎ አስፈራራኝ እንጂ"አለ በቅሬታ
‹‹ማሙሽ ገቢናውን ልቀቅላትና ከኃላ ግባ አለው ››አብዬት ጣልቃ ገብቶ አዘዘው።
አረ ተወው እኃላ ሆናለው ብላ ከፍታ ገባች..አቢዬትም ገባና መኪናዋን አንቀሳቀሰ
"አብዬት በእስፓኪዬ ወደኃላ አየተመለከታት ነው።ከስታለች..መክሳት ብቻ ሳይሆን ገርጥታለች አይኖቾ ጉድጉድ ከማለታቸው በላይ ቁዝዝ ብለዋል...ለቀናት የረባ እንቅልፍ እንዳልተኛች ያስታውቃል...የጤናዋም ሁኔታ አሳስቦታል።
"እንዴ ወደቤት አይደለ እንዴ የምንሄደው ?ነው ወይስ አድራሻ ቀየራችሁ?"ስትል ጠየቀች።የዚህ ጥያቄ መነሻ አብዬት መኪናዋን እየነዳበት ያለው አቅጣጫ ከቤታቸው አቅጣጫ ጋር ስላልገጠመላት ነው።
"አይ እዛው ነን...እግረ መንገዳችንን እዚህ ሰፈር ጉዳይ ቢጤ ስላለችኝ ነው።አያቆየንም።"
"ጉዳይ ካለህ ታዲያ እኛ ምን አገባን ..አውርደን እና በታክሲ እንሄዳለን"አለ ካሳ ተበሳጭቶ
ዶ/ሯ ደነገጠችና "አረ ችግር የለም..እቤትስ ሄደን ምን እንሰራለን ..እንደውም በዚህ ምሽት ነፍሻማ አየር ከተማውን መዞር አስደሳች ነው...በዛ ላይ አንድ ክፍል ውስጥ ታፍኜ መሠንበቴን አትርሳ"
"ላንቺው ብዬ ነው"
"ለእሷ ብለህ ምን...?"
"ይሄንን ያንተን አስቀያሚ ፊት ለረጂም ሰዓት እያየች እንዳትፈራ ብዬ ነው...ይሄንን ፊት ይዘህ ስታፈቅራት ግን ትንሽ አታሳዝንህም?"
በካሳ ሰቅጣጭ ንግግር ዶክተሯ የምትገባበት ጠፋት.. የአብዬትን ንዴት ለማየት አይኖቾን በፈራ ተባ ወደእሱ ስትልካቸውእሱ በካሳ ንግግር እየሳቀ ነው..መኪናውን አቆመ ፡፡
"ሆስፒታል ደግሞ ምን እንሰራለን?"አሁንን በንጭንጭ ቃና ጥያቄውን የሰነዘረው ካሳ ነው
"አስቀያሚ ፊቴን እንዲያስተካክሉልኝ"
ከእግሩ ስር የነበረ ጥቁር ፔስታል አነሳና ለዶክተር ወደኃላ አቀበላት
"ምንድነው...?››
‹‹ወደ ውስጥ አብረን ስለምንገባ እራስሺን ቀይሪ››
ፔስታሉን ውስጥ ያሉ ቁሳቁሶችን ጎኗ ካለ ወንበር ላይ ዘረገፈችና በየተራ አየቻቸው።
"አንተ እነዚ ዕቃዎች አሁንም አሉ?"
"ከዚህ መከራ ሙሉ በሙሉ እስክንወጣ ያስፈልጉናል ብዬ አስቀምጬቸው ነበር ይሄው ዛሬ አስፈለጉን..››እቃዎቹን
ስታይ ከገዳዬቾ ሽሽት እንዴት እሱ እጅ እንደገባቸ እነዚህን እራስን መቀየሪያ የገዛላት ጊዜ ተሠምቶት የነበረው ስሜት ሁሉም ፊቷ ላይ ድቅን አለ..ፀጉሩን አጠለቀች...መነፅሯን ሰካች...በአንገቷ ዙሪያ ሻርፗን ጠመጠመችና አጠናቀቀች
አቢዬትም ከገቢናውን ለቆ ወረደና የዶ/ሯን በራፍ ከፈተ
‹‹ውረጂ ዶክተር››
ወረደች..
ካሳ "እኔም ልምጣ እንዴ..?"
"ቦሮጫህን ቀደው እንዲያስወግድልህ ከፈለክ ና"
"አይ እንደውም ትቼዋለው.. የመድሀኒት ሽታ በጣም ነው የሚያስጠላኝ።
ትተውት ጎን ለጎን ሆነው ወደውስጥ መጓዝ ጀመሩ
"ለምንድነው ግን ወደእዚህ የመጣነው?"ጠየቀችው
"ታመሽና እራስሽን ስተሽ እንደነበር ሰምቼያለው ምክንያቱን ማወቅ አለብን።››
"እና ነገ ተነገ ወዲያ አይደርስም ነበር?"
👍22❤3🥰3😁1
"አይ ...የጤና ጉዳይ ለነገ አይባልም...አሁኑኑ መመርመር አለብሽ"
"ታውቃለህ አይደል ...በጣም ምርጥ ሰው ነህ"
"መስሎሽ ነው...ምርጥ መሆን ፈልጌ አይምሰልሽ ..ፈርዶብኝ እንጂ"
‹‹ማለት?›› አለችው የሚለው ስላልገባት
"አይ ምንም እንዲሁ ነው"
በዚህ ጊዜ ካርድ የምትቆርጠዋ ልጅ ፊት ለፋት ደርሰው ነበረ
"ካርድ ፈልገን ነበር"
"ላንተነው ለእሷ"
"ለእሷ"
"እስኪሪፕቶዋን ካርድ ላይ ቀስራ ለመፃፍ እየተዘጋጀች ‹‹ስም ስትል ጠየቀች "
ዶክተሯ ስሟን ለመናገር አፎን ስትከፍት
"እፅብ."ብሎ ነገራት አብዬት
ዶክተሯ በገረሜታ ቀና ብላ አየችው
"እፅብ ማ.."
"እፅብ አብዬት"ካርዳቸውን ተቀብለው እየተስሳሳቁ ወደተዘጋጀው ተራ ወደመጠበቂያ ወንበር ሄደው ጎን ለጎን ተቀመጡ
"እፅብ ማነች አለቺው?"
"እፅብ ልጄ"
"እንዴ ልጅ አለህ እንዴ ?"
"አይ ለአሁኑ የለኝም...ወደፊት ከኖረኝ ብዬ ነው ቀድሜ ስም ያወጣሁላት"
በዚህ ጊዜ ስሞ ተጠራና ለምርመራ ገባች..አጠቃላይ ምርመራው 40 ደቂቃ ፈጀ ጨርሳ ስትወጣ ግን ...ጎብጣ ነበር...እንባዋ ከቁጥጥሯ ወጭ ይረግፋል...አብዬት ሁኔታዋን ሲያይ በጣም ደነገጠ..እንደምንም ደግፎ መኪናው ጋር ወሰደና ወደ ውስጥ አስገባት...ተከትሎት ገባና ከጎኖ ቁጭ አለ፡፡
"እዛ ከጎኖ የተለጠፍከው መኪናውን ማን እንዲነዳልህ ነው?"አለው ካሳ
‹‹ችላ አለውና"አረ ባክሽ ዶክተር ምንድነው የተፈጠረው?"
ደረቱ ላይ ተለጥፋ መንሰቅሰቅ ጀመረች።ካሳ እንዴ አንተ ምን አድርገሀት"እያለ ገቢናውን ለቆ ወረደና እነሱ ወዳሉበት የኃላ ወንበር ገባ ።መሀከል አደረጎት
‹‹ዶክተር ምን አይነት በሽታ ቢሉሽ ነው እንዲህ በአንዴ ማቅ የለበሽው...?ይሄውልሽ አንቺ በዚህ አስራአምስት ቀን ውስጥ ከስንት ወጥመድ ከስንት ሞት አምልጠሻል ...እና ምን አዲስ ነገር መጣ ? እነዛ ጭራቆችን ያሸነፍሽ በሽታ ማሸነፍ ያቅትሻል?››
"ደግሞ ከአሁን ወዲያ እኛም ከጎንሽ ነን ...መቼም ቢሆን መቼ ብቻሽን አንተውሽም..."
"አዎ አንተውሽም ..እንዲ እንደአሁኑ በግራና በቀኝ ደግፈን አስከመጨረሻው እንንከባከብሻለን"ካሳ ቃል ገባ፡፡
"ከጎኔ እንደሆናችሁ አውቃለው..ግን ያልገባችሁ ነገር አለ"
"እኮ እንዲገባን ንገሪና እየለመንሽ እኮ ነው?"አብዬት ነው በጭንቀት የጠየቃት
"አርግዤለሁ"
"አርግዤለሁ ማለት ..?ማርገዝ ምንድነው..?ከእኔ ጋር አድርገን ነበር እንዴ..?.ነው ከእኔ ተደብቃችሁ አደረጋችው...ካሳ አብዬት ላይ አፈጠጠበት
‹አብዬት ተናደደ‹‹እስቲ አሁን እንኳን ቢሆን ዝም በል …ዶ/ር አልገባኝም›
‹እኔም አልገባኝም..የ7 ሰማንት እርጉዝ ነኝ…የዛን አውሬ ልጅ በሆዴ ተሸክሜለሁ››
‹‹የፈጣሪ ያለህ››አለ አብዬት ለ30 ደቂቃ ሁሉም እርስ በርስ እንደተጣበቁ በመቀመጥ ከመተከዝና ከመብሰልሰል ውጭ የተነጋገሩት ነገር አልነበረም፡፡
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
"ታውቃለህ አይደል ...በጣም ምርጥ ሰው ነህ"
"መስሎሽ ነው...ምርጥ መሆን ፈልጌ አይምሰልሽ ..ፈርዶብኝ እንጂ"
‹‹ማለት?›› አለችው የሚለው ስላልገባት
"አይ ምንም እንዲሁ ነው"
በዚህ ጊዜ ካርድ የምትቆርጠዋ ልጅ ፊት ለፋት ደርሰው ነበረ
"ካርድ ፈልገን ነበር"
"ላንተነው ለእሷ"
"ለእሷ"
"እስኪሪፕቶዋን ካርድ ላይ ቀስራ ለመፃፍ እየተዘጋጀች ‹‹ስም ስትል ጠየቀች "
ዶክተሯ ስሟን ለመናገር አፎን ስትከፍት
"እፅብ."ብሎ ነገራት አብዬት
ዶክተሯ በገረሜታ ቀና ብላ አየችው
"እፅብ ማ.."
"እፅብ አብዬት"ካርዳቸውን ተቀብለው እየተስሳሳቁ ወደተዘጋጀው ተራ ወደመጠበቂያ ወንበር ሄደው ጎን ለጎን ተቀመጡ
"እፅብ ማነች አለቺው?"
"እፅብ ልጄ"
"እንዴ ልጅ አለህ እንዴ ?"
"አይ ለአሁኑ የለኝም...ወደፊት ከኖረኝ ብዬ ነው ቀድሜ ስም ያወጣሁላት"
በዚህ ጊዜ ስሞ ተጠራና ለምርመራ ገባች..አጠቃላይ ምርመራው 40 ደቂቃ ፈጀ ጨርሳ ስትወጣ ግን ...ጎብጣ ነበር...እንባዋ ከቁጥጥሯ ወጭ ይረግፋል...አብዬት ሁኔታዋን ሲያይ በጣም ደነገጠ..እንደምንም ደግፎ መኪናው ጋር ወሰደና ወደ ውስጥ አስገባት...ተከትሎት ገባና ከጎኖ ቁጭ አለ፡፡
"እዛ ከጎኖ የተለጠፍከው መኪናውን ማን እንዲነዳልህ ነው?"አለው ካሳ
‹‹ችላ አለውና"አረ ባክሽ ዶክተር ምንድነው የተፈጠረው?"
ደረቱ ላይ ተለጥፋ መንሰቅሰቅ ጀመረች።ካሳ እንዴ አንተ ምን አድርገሀት"እያለ ገቢናውን ለቆ ወረደና እነሱ ወዳሉበት የኃላ ወንበር ገባ ።መሀከል አደረጎት
‹‹ዶክተር ምን አይነት በሽታ ቢሉሽ ነው እንዲህ በአንዴ ማቅ የለበሽው...?ይሄውልሽ አንቺ በዚህ አስራአምስት ቀን ውስጥ ከስንት ወጥመድ ከስንት ሞት አምልጠሻል ...እና ምን አዲስ ነገር መጣ ? እነዛ ጭራቆችን ያሸነፍሽ በሽታ ማሸነፍ ያቅትሻል?››
"ደግሞ ከአሁን ወዲያ እኛም ከጎንሽ ነን ...መቼም ቢሆን መቼ ብቻሽን አንተውሽም..."
"አዎ አንተውሽም ..እንዲ እንደአሁኑ በግራና በቀኝ ደግፈን አስከመጨረሻው እንንከባከብሻለን"ካሳ ቃል ገባ፡፡
"ከጎኔ እንደሆናችሁ አውቃለው..ግን ያልገባችሁ ነገር አለ"
"እኮ እንዲገባን ንገሪና እየለመንሽ እኮ ነው?"አብዬት ነው በጭንቀት የጠየቃት
"አርግዤለሁ"
"አርግዤለሁ ማለት ..?ማርገዝ ምንድነው..?ከእኔ ጋር አድርገን ነበር እንዴ..?.ነው ከእኔ ተደብቃችሁ አደረጋችው...ካሳ አብዬት ላይ አፈጠጠበት
‹አብዬት ተናደደ‹‹እስቲ አሁን እንኳን ቢሆን ዝም በል …ዶ/ር አልገባኝም›
‹እኔም አልገባኝም..የ7 ሰማንት እርጉዝ ነኝ…የዛን አውሬ ልጅ በሆዴ ተሸክሜለሁ››
‹‹የፈጣሪ ያለህ››አለ አብዬት ለ30 ደቂቃ ሁሉም እርስ በርስ እንደተጣበቁ በመቀመጥ ከመተከዝና ከመብሰልሰል ውጭ የተነጋገሩት ነገር አልነበረም፡፡
ይቀጥላል......
ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ
ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍29❤4😁1
#ኢቫንጋዲ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ቀኑ ቅዳሜ ነው። ሴቬሊያ ከተማ ላይ አንዣቦ የከረመው ዳመና ተበታትኖ ሰማያዊው ሰማይ በፀሐይ ብርሃን ተጥለቅልቆ ኗሪው በደስታ ሲንቀሳቀስ ይታያል።
ሶራ ከመኝው የተነሳው ዘግየት ብሎ ሲሆን ከመኝታው ተነስቶ ሳሎኑ ሲገባ አብረውት የሚኖሩት ሁለቱ የክፍል ጓደኞቹ
ሞዛምቢካዊው ኢናሲዬ እና ሴኔጋላው ዲያንካ ሲከራከሩ አገኛቸው:
“...አየህ የኛ የአፍሪካውያን ችግር በእለት ችግሮቻችን ላይ ካልሆነ በህልማችን በሐሳባችን... ላይ በትዕግስት መወያየት
መከራከር አንችልም: በግልፍተኝነት ስለ ዛሬ እናወራለን ዛሬ በምንፈፅመው እናዝናለን ወይንም እንረካለን።
ዛሬን ከትናንትና ከነገ ጋር ማነፃፀር ስለማንችል መቻቻሉም ያቅተናል: እና እኛ አፍሪውያን ከጊዜ የቁም እስር እራሳችንን ነፃ
አድርገን ጊዜን መጠቀም ስንጀምር! ሽንፈትና ድልን ልዩነቱን ስናውቅ በቅድሚያ ችግሮቻችንን እንፈታለን…” አለ ሞዛምቢካዊው
ኢናሲዬ:
“…በሃሣብህ እኮ እስማማለሁ፡ ችግሩ ግን እንደ ቡችላ ያለው አይናችንን ለመክፈት ገና ስናስብ የሰለጠኑት ህዝቦች ባለፉት ጊዜያት ከተጠቀሙበት መሳሪያ በተሻለና በረከሰ የረቀቀ መረብ እየጠለፉ ይጥሉናል: ለዚህ መፍትሄው ምን
ይሁን ነው? እኛ ፊደል እንዴት እንቁጠር ስንል አንዱ እርስ በራሳችን እንማማር ሌላው የሰለጠኑት ህዝቦች እንዲያስተምሩን
እንለምን... ሲል ጊዜያት ከነፉ፤ የጥቁር ህዝብ ህልም እንደ
ኪሊማንጃሮ ተራራ ቢከመር ጠብታ ተግባር ካልወጣው! አንዱ ሌላውን ወንድሙን ገሉ ማቅራራቱንና መፎከሩን ካላቆምንና ራሳችንን መግዛት ካቃተን ጥሩ ተገዥ መሆን ይሻለናል” ብሎ
የምፀት ሳቁን ሳቀ ሁለቱም ተሳሳቁ፡
“ጥሩ! ማን በማን ላይ እንደሳቀ ዳኝነቱን ወደፊት
እስከገልፅ አንዴ ይቅርታ ይደረግልኝ..."
“ሶራ! ሁለቱም እንደተመካከሩ ሀሉ በአድናቆት ዞረው
ጠሩትና
ዛሬ ምነው ምሽግን አለቅም ብለህ ዋልህ? ያች ኢትዬ
ስፔናዊት የምትሰራው የቤት ስራም ሰጥታህ
ነበር መሰል ሞዛምቢካዊው ኢናሊዬ የጓደኛውን ጉልበት መታ አድርጎ ቤቱን
ለሁለት በሣቅ አነቃነቁት።
ከባድ የቤት ሥራ ነበር የሰጠችኝ፡ ጥያቄዋን ሽ ጊዜ አነበብኩት በቃሌ አነበብኩት! መልሱ ግን ጠፋኝ። ጥያቄዋን
ካለእሷ ሊመልሰው የሚችል የለም:"
“ስለዚህ መልሱን ከመምህርት ኢትዮ ስፔናዊት ለማግኘት
ልትሄድ ነዋ!” ነዋ!
ቶሉ መሄድ! የጠፋኝን ቶሉ ማወቅ ከዚያ ጎበዝ
ደቀ መዝሙሯ መሆን እፈልጋለሁ።” የሁለቱንም ትከሻ መታ መ+ አድርጎ። ወደ ውስጥ ገብቶ ለባብሶ ወጣና፡-
“አጭርና ያልተንዛዛ አስተያየት አላማረብኝም አላቸዎሸ በየተራ እያያቸው።
“መልሱን ካለ አንድ ሰው አይመልሰውም" ሲል ዲያንካ
“እሷም መምህርት ኢትዮ ስፔናዊት ብቻ ናት..." አለ ኢናልዬ
“ትክክል!'' ብሎ የኢናሲዬን ትከሻ መታ መታ አድርጎ በሩን ከፍቶ ሲወጣ ሳቃቸው ከኋላው ተከተለው
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሶራና ኮንችት ከተዋወቁ በኋላ ኮንችት ቤት ማድሪድ
በሚገኘው ፒካሶ ሆቴል... ደጋግመው ተገናኝተዋል። ኮንችት በሶራ ግልፅነት በጎደለው ይሉኝታ በተበተበው ባህሪው ብዙ ጊዜ ትበሽቃለች።
ሶራ መብላት ትፈልጋለህ?" ስትለው
“አንችስ?” ሲላት በብስጭት
"እፈልጋለሁ! ወይንም አልፈልግም። ስለእኔ እኔ ስለአንተ ደግሞ አንተ መመለስ በቃ። የአንተ መፈለግ አለመፈለግ ከእኔ ጋር ምን አገናኘው" ትለዋለች
“የዛሬ ግብዣ የኔ ነው"
“ጥሩ ስለግብዣ ሃሳብህ አመሰግንሃለሁ። የት ነው የምትጋብዘኝ?
“የት ልጋብዝሽ?”
“ኦ! - አምላኬ!” በንዴት ትጦፍና፦
“ሰውን ልትጋብዝ ስትፈልግ በቅድሚያ የት ምን
እንደምትጋብዘው አስብ እሽ ፊቷ በንዴት እንደቀላ ትነግረዋለች
“ምነው ዝም አልሽ?
“ለምን ጠየቅከኝ?
“ስለማትጫወቺ ስለማትስቂ...”
"ሰው ቤት ከመሄድህ በፊት ልትገናኙ መቻል አለመቻላችሁን ደውለህ ፈቃድ ጠይቅ ! እኛ ሰዎች ለስራ ለጨዋታ
ለእረፍት... የምንመድበው ጊዜ አለ:: ሰዎችን በፕርግራማቸው
እንዳይጠቀሙ እንቅፋት መሆን ትልቅ ሃጢያት ነው: ገባህ!” ትለዋለች።
“የያዝሽውን እቃ ልያዝልሽ?
“ለምን?
“ይከብድሻል…”
“ፖልፋቮር /ይቅርታ/ እኔ ጡጦ የምታጠባው ህፃን ልጅህ አይደለሁም የሚከብደኝን መጀመሪያውንም አልይዝም።እሺ
በንዴት ትንጨረጨርበታለች ሶራ ባህሪዋ ሙልጭልጭ ይልበታል ሲያዝንላት ሲንከባከባት ሲሞክርና እንዲቀራረቡ ጥረት ሲያደርግ? አባባሉን በተቃራኒ ተረድታ በግሳፄ የህሊና ድዱን በርግጫ
ታወልቀዋለች:
እሱ ግን ይችላታል: ሆዱ እየተቀየመ አንደበቱ ግን
ያልፋታል።
“ዲስኮ ዳንስ ቤት ብዙ መቆየት አልወድም"
“ሶራ! ከኔ ጋር ግን'ኮ አብረህ…"
“ላስከፋሽ ስላልፈለግሁ"
“እብድ ነህ! የማትፈልገውን ለኔ ብለህ የምታደርግ?”
“ብቻሽን ትቼሽ መሄድ ስላልፈለግሁ"
“በቃህ አንተ ኖርህ አልኖር ለኔ ለውጥ የለውም 7
ገባህ! መዝናናት ስፈልግ ዘበኛ አላስከትልም: ማንንም ካለፍላጎቱ እንደ
ከዘራ ቆልምሜ የኔ ምርኩዝ ማድረግ አልሻም.." ታፈጥበታለች።
አብሯት ለመሆን እንደሚጓጓው ሁሉ ከሷ መለየቱንም ይፈልገዋል: ልዩነታቸው ብዙ ነው።
ኮንችት ባህሪው ግልፅ
ነው ሣቋን አንደ ጥሩ ሙዚቃ በስሜት ይደንስበታል: ችግሩ ድንገት እሳት ወዲያው ውሃ
ትሆንበታለች:: እሳት ስትሆን ሊሸሻት ይፈልጋል! ውሃ ስትሆን ደግሞ እንደ ፀበል በጨዋታዋ ይጠመቃል!
ሶራ ሜዳ ይሁን ገደል ስሜቱ በደመ ነፍሱ ሲጋልብም እሷ
ለሁሉም ነገር ምክንያት ትፈልጋለች: እየተሞላቀቀች
ጭኖችዋን ፓንቷን.. ስታሳየውና ጉሮሮውን ስታስጮህበት ስሜቱን
ስታስነጥስበት ትቆይና መላውን ሳትለው ድንገት
“መተኛት እፈልጋለሁ" ትለዋለች።
ትንሽ አንጫወትም?"
...የሰው ፍላጎት ሊገባህ ይገባል እሽ?" ቀልቡን ገፋበት መኝታ ቤቷ ትገባለች። እሱም ወጥቶ ይሄዳል። ቤቱ ሲሄድ ግን
ህሊናው እረፍት ሲነሳው ሰውነቱ እንደ እሳት ሲቀጣጠልበት
መታጠቢያ ቤት ይገባና ቀዝቃዛ ሻወር ገላው ላይ ያፈሳል፡ ለአያቷ
አገር ለኢትዮጵያ ያላት ናፍቆት ግልፅነቷ ሳቋ… ተክለ ቁመናዋ
እያወዛወዘው ሲያንጨዋልለው ፍላጎቱ ለእሷ ያለው ቀረቤታ
ከጓደኝነት ያለፈ ይሆንበታል።
ኮንችት ደጋግማ
የነገረችው ስሜትህንና ፍላጎትህን አትደብቅ ነው። ስለዚህ እየዋለ ባደረ ቁጥር ናፍቆቱ ጤና ሲነሳው
ስሜቱን ሊገልፅላት አሰበ: ድፍረቱና አጋጣሚው ጠፍቶ ለቀናት ተሰቃዩ:: አንድ ቀን ግን ደፈረ:
“ኮንችት?”
“አቤት" ያ እንደ ንስር አይን ተልቆ የሚበረበረው አይኗ
ከመናገሩ በፊት እየበሳሳው ውስጠ ሚስጥሩን አየበት።
“አፈቅርሻለሁ አላት ባጭሩ። ኮንችት ግን ይህን ስሜቱንና አባባሉን ቀደም ብላ እንደተረዳች ሀሉ፡
“ለምን አፈቀርኸኝ? በአባባሉ ሳትደነቅ ጠየቀችው
ተቁነጠነጠ! ግልጽ ሁን ብላ ወትውታ ግልፅ ሲሆን ደግሞ ዓለምን ያስጨነቀ ጥያቄ “ለምን?" እያለች በማስቸገሯ ተማረረባት።
ለምን አፈቀርኝ? ደግማ ጠየቀችው
“አስተሳሰብሽ ደስ ይለኛል” አንገቱ ላይ እንደቆሙበት ውሻ አይኑ እየተቁለጨለጨ መለሰላት።
“አስተሳሰቤን ገና መች ተረዳኸው። እኔ የማስበው ለአንተ እንግዳ ነው: የአንተ ደግሞ ለእኔ እንዲሁ አይገባኝም። ታዲያ
ሳንግባባ እንዴት አስተሳሰቤን አውቀህ አፈቀርኸኝ:"
“የምልሽ ፀባይሽም ደስ ይለኛል"
“ፀባዬ ምን አይነት ነው?"
“ግልፅ
“ፀባዬን እንዳልወደድኸው ግን ብዙ ምልክቶች አይቸብሃለሁ
"ቁመናሽ ደስ ይለኛል..."
“አንድን ሰው በማፍቀርና በመፈለግ መካከል ያለውን ልይነት ግን ታውቃለህ?"
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#በፍቅረማርቆስ_ደስታ
ቀኑ ቅዳሜ ነው። ሴቬሊያ ከተማ ላይ አንዣቦ የከረመው ዳመና ተበታትኖ ሰማያዊው ሰማይ በፀሐይ ብርሃን ተጥለቅልቆ ኗሪው በደስታ ሲንቀሳቀስ ይታያል።
ሶራ ከመኝው የተነሳው ዘግየት ብሎ ሲሆን ከመኝታው ተነስቶ ሳሎኑ ሲገባ አብረውት የሚኖሩት ሁለቱ የክፍል ጓደኞቹ
ሞዛምቢካዊው ኢናሲዬ እና ሴኔጋላው ዲያንካ ሲከራከሩ አገኛቸው:
“...አየህ የኛ የአፍሪካውያን ችግር በእለት ችግሮቻችን ላይ ካልሆነ በህልማችን በሐሳባችን... ላይ በትዕግስት መወያየት
መከራከር አንችልም: በግልፍተኝነት ስለ ዛሬ እናወራለን ዛሬ በምንፈፅመው እናዝናለን ወይንም እንረካለን።
ዛሬን ከትናንትና ከነገ ጋር ማነፃፀር ስለማንችል መቻቻሉም ያቅተናል: እና እኛ አፍሪውያን ከጊዜ የቁም እስር እራሳችንን ነፃ
አድርገን ጊዜን መጠቀም ስንጀምር! ሽንፈትና ድልን ልዩነቱን ስናውቅ በቅድሚያ ችግሮቻችንን እንፈታለን…” አለ ሞዛምቢካዊው
ኢናሲዬ:
“…በሃሣብህ እኮ እስማማለሁ፡ ችግሩ ግን እንደ ቡችላ ያለው አይናችንን ለመክፈት ገና ስናስብ የሰለጠኑት ህዝቦች ባለፉት ጊዜያት ከተጠቀሙበት መሳሪያ በተሻለና በረከሰ የረቀቀ መረብ እየጠለፉ ይጥሉናል: ለዚህ መፍትሄው ምን
ይሁን ነው? እኛ ፊደል እንዴት እንቁጠር ስንል አንዱ እርስ በራሳችን እንማማር ሌላው የሰለጠኑት ህዝቦች እንዲያስተምሩን
እንለምን... ሲል ጊዜያት ከነፉ፤ የጥቁር ህዝብ ህልም እንደ
ኪሊማንጃሮ ተራራ ቢከመር ጠብታ ተግባር ካልወጣው! አንዱ ሌላውን ወንድሙን ገሉ ማቅራራቱንና መፎከሩን ካላቆምንና ራሳችንን መግዛት ካቃተን ጥሩ ተገዥ መሆን ይሻለናል” ብሎ
የምፀት ሳቁን ሳቀ ሁለቱም ተሳሳቁ፡
“ጥሩ! ማን በማን ላይ እንደሳቀ ዳኝነቱን ወደፊት
እስከገልፅ አንዴ ይቅርታ ይደረግልኝ..."
“ሶራ! ሁለቱም እንደተመካከሩ ሀሉ በአድናቆት ዞረው
ጠሩትና
ዛሬ ምነው ምሽግን አለቅም ብለህ ዋልህ? ያች ኢትዬ
ስፔናዊት የምትሰራው የቤት ስራም ሰጥታህ
ነበር መሰል ሞዛምቢካዊው ኢናሊዬ የጓደኛውን ጉልበት መታ አድርጎ ቤቱን
ለሁለት በሣቅ አነቃነቁት።
ከባድ የቤት ሥራ ነበር የሰጠችኝ፡ ጥያቄዋን ሽ ጊዜ አነበብኩት በቃሌ አነበብኩት! መልሱ ግን ጠፋኝ። ጥያቄዋን
ካለእሷ ሊመልሰው የሚችል የለም:"
“ስለዚህ መልሱን ከመምህርት ኢትዮ ስፔናዊት ለማግኘት
ልትሄድ ነዋ!” ነዋ!
ቶሉ መሄድ! የጠፋኝን ቶሉ ማወቅ ከዚያ ጎበዝ
ደቀ መዝሙሯ መሆን እፈልጋለሁ።” የሁለቱንም ትከሻ መታ መ+ አድርጎ። ወደ ውስጥ ገብቶ ለባብሶ ወጣና፡-
“አጭርና ያልተንዛዛ አስተያየት አላማረብኝም አላቸዎሸ በየተራ እያያቸው።
“መልሱን ካለ አንድ ሰው አይመልሰውም" ሲል ዲያንካ
“እሷም መምህርት ኢትዮ ስፔናዊት ብቻ ናት..." አለ ኢናልዬ
“ትክክል!'' ብሎ የኢናሲዬን ትከሻ መታ መታ አድርጎ በሩን ከፍቶ ሲወጣ ሳቃቸው ከኋላው ተከተለው
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሶራና ኮንችት ከተዋወቁ በኋላ ኮንችት ቤት ማድሪድ
በሚገኘው ፒካሶ ሆቴል... ደጋግመው ተገናኝተዋል። ኮንችት በሶራ ግልፅነት በጎደለው ይሉኝታ በተበተበው ባህሪው ብዙ ጊዜ ትበሽቃለች።
ሶራ መብላት ትፈልጋለህ?" ስትለው
“አንችስ?” ሲላት በብስጭት
"እፈልጋለሁ! ወይንም አልፈልግም። ስለእኔ እኔ ስለአንተ ደግሞ አንተ መመለስ በቃ። የአንተ መፈለግ አለመፈለግ ከእኔ ጋር ምን አገናኘው" ትለዋለች
“የዛሬ ግብዣ የኔ ነው"
“ጥሩ ስለግብዣ ሃሳብህ አመሰግንሃለሁ። የት ነው የምትጋብዘኝ?
“የት ልጋብዝሽ?”
“ኦ! - አምላኬ!” በንዴት ትጦፍና፦
“ሰውን ልትጋብዝ ስትፈልግ በቅድሚያ የት ምን
እንደምትጋብዘው አስብ እሽ ፊቷ በንዴት እንደቀላ ትነግረዋለች
“ምነው ዝም አልሽ?
“ለምን ጠየቅከኝ?
“ስለማትጫወቺ ስለማትስቂ...”
"ሰው ቤት ከመሄድህ በፊት ልትገናኙ መቻል አለመቻላችሁን ደውለህ ፈቃድ ጠይቅ ! እኛ ሰዎች ለስራ ለጨዋታ
ለእረፍት... የምንመድበው ጊዜ አለ:: ሰዎችን በፕርግራማቸው
እንዳይጠቀሙ እንቅፋት መሆን ትልቅ ሃጢያት ነው: ገባህ!” ትለዋለች።
“የያዝሽውን እቃ ልያዝልሽ?
“ለምን?
“ይከብድሻል…”
“ፖልፋቮር /ይቅርታ/ እኔ ጡጦ የምታጠባው ህፃን ልጅህ አይደለሁም የሚከብደኝን መጀመሪያውንም አልይዝም።እሺ
በንዴት ትንጨረጨርበታለች ሶራ ባህሪዋ ሙልጭልጭ ይልበታል ሲያዝንላት ሲንከባከባት ሲሞክርና እንዲቀራረቡ ጥረት ሲያደርግ? አባባሉን በተቃራኒ ተረድታ በግሳፄ የህሊና ድዱን በርግጫ
ታወልቀዋለች:
እሱ ግን ይችላታል: ሆዱ እየተቀየመ አንደበቱ ግን
ያልፋታል።
“ዲስኮ ዳንስ ቤት ብዙ መቆየት አልወድም"
“ሶራ! ከኔ ጋር ግን'ኮ አብረህ…"
“ላስከፋሽ ስላልፈለግሁ"
“እብድ ነህ! የማትፈልገውን ለኔ ብለህ የምታደርግ?”
“ብቻሽን ትቼሽ መሄድ ስላልፈለግሁ"
“በቃህ አንተ ኖርህ አልኖር ለኔ ለውጥ የለውም 7
ገባህ! መዝናናት ስፈልግ ዘበኛ አላስከትልም: ማንንም ካለፍላጎቱ እንደ
ከዘራ ቆልምሜ የኔ ምርኩዝ ማድረግ አልሻም.." ታፈጥበታለች።
አብሯት ለመሆን እንደሚጓጓው ሁሉ ከሷ መለየቱንም ይፈልገዋል: ልዩነታቸው ብዙ ነው።
ኮንችት ባህሪው ግልፅ
ነው ሣቋን አንደ ጥሩ ሙዚቃ በስሜት ይደንስበታል: ችግሩ ድንገት እሳት ወዲያው ውሃ
ትሆንበታለች:: እሳት ስትሆን ሊሸሻት ይፈልጋል! ውሃ ስትሆን ደግሞ እንደ ፀበል በጨዋታዋ ይጠመቃል!
ሶራ ሜዳ ይሁን ገደል ስሜቱ በደመ ነፍሱ ሲጋልብም እሷ
ለሁሉም ነገር ምክንያት ትፈልጋለች: እየተሞላቀቀች
ጭኖችዋን ፓንቷን.. ስታሳየውና ጉሮሮውን ስታስጮህበት ስሜቱን
ስታስነጥስበት ትቆይና መላውን ሳትለው ድንገት
“መተኛት እፈልጋለሁ" ትለዋለች።
ትንሽ አንጫወትም?"
...የሰው ፍላጎት ሊገባህ ይገባል እሽ?" ቀልቡን ገፋበት መኝታ ቤቷ ትገባለች። እሱም ወጥቶ ይሄዳል። ቤቱ ሲሄድ ግን
ህሊናው እረፍት ሲነሳው ሰውነቱ እንደ እሳት ሲቀጣጠልበት
መታጠቢያ ቤት ይገባና ቀዝቃዛ ሻወር ገላው ላይ ያፈሳል፡ ለአያቷ
አገር ለኢትዮጵያ ያላት ናፍቆት ግልፅነቷ ሳቋ… ተክለ ቁመናዋ
እያወዛወዘው ሲያንጨዋልለው ፍላጎቱ ለእሷ ያለው ቀረቤታ
ከጓደኝነት ያለፈ ይሆንበታል።
ኮንችት ደጋግማ
የነገረችው ስሜትህንና ፍላጎትህን አትደብቅ ነው። ስለዚህ እየዋለ ባደረ ቁጥር ናፍቆቱ ጤና ሲነሳው
ስሜቱን ሊገልፅላት አሰበ: ድፍረቱና አጋጣሚው ጠፍቶ ለቀናት ተሰቃዩ:: አንድ ቀን ግን ደፈረ:
“ኮንችት?”
“አቤት" ያ እንደ ንስር አይን ተልቆ የሚበረበረው አይኗ
ከመናገሩ በፊት እየበሳሳው ውስጠ ሚስጥሩን አየበት።
“አፈቅርሻለሁ አላት ባጭሩ። ኮንችት ግን ይህን ስሜቱንና አባባሉን ቀደም ብላ እንደተረዳች ሀሉ፡
“ለምን አፈቀርኸኝ? በአባባሉ ሳትደነቅ ጠየቀችው
ተቁነጠነጠ! ግልጽ ሁን ብላ ወትውታ ግልፅ ሲሆን ደግሞ ዓለምን ያስጨነቀ ጥያቄ “ለምን?" እያለች በማስቸገሯ ተማረረባት።
ለምን አፈቀርኝ? ደግማ ጠየቀችው
“አስተሳሰብሽ ደስ ይለኛል” አንገቱ ላይ እንደቆሙበት ውሻ አይኑ እየተቁለጨለጨ መለሰላት።
“አስተሳሰቤን ገና መች ተረዳኸው። እኔ የማስበው ለአንተ እንግዳ ነው: የአንተ ደግሞ ለእኔ እንዲሁ አይገባኝም። ታዲያ
ሳንግባባ እንዴት አስተሳሰቤን አውቀህ አፈቀርኸኝ:"
“የምልሽ ፀባይሽም ደስ ይለኛል"
“ፀባዬ ምን አይነት ነው?"
“ግልፅ
“ፀባዬን እንዳልወደድኸው ግን ብዙ ምልክቶች አይቸብሃለሁ
"ቁመናሽ ደስ ይለኛል..."
“አንድን ሰው በማፍቀርና በመፈለግ መካከል ያለውን ልይነት ግን ታውቃለህ?"
👍27👎1
“እሱን'ኳ በሚገባ አውቃለሁ።"
“አይመስለኝም፤ ቁመናዬን ወደኸዋል። ባህሪዬንና
አስተሳሰቤን ግን ለአንተ ብዙው እንግዳ ነው እና ቢያንስ አትናፍቀውም::
አንተ ከአገርህ ከለመድኸው ባህል ርቀህ ስለመጣህ ብቸኝነትን ይሰማሃል: በአጋጣሚ ደግሞ ብቸኝነትህን የሚቀንስልህ
የሚጋራህና ደስታ የሚፈጥርልህ ሰው ስትፈልግ እኔን አገኘህ። ደስ
አለህ እና እኔን ትፈልገኛለህ እንጂ አታፈቅረኝም: ፍቅር የሚገዛው በህሊና ነው። ወሲባዊ የስሜት ፍላጎት ቢሆን እንኳን በስሜት
ቅፅበታዊ ደስታን ለማግኘት እስከሆነ ድረስ የፍቅር ምልክት ሊሆን
አይችልም::
"...በህይወቴ አፈቀርሁሽ ከመባል ሌላ እሚያስደስተኝ ነገር የሚኖር አይመስለኝም: ጓደኞቼ አንተን አፈቅርሻለሁ ስትለኝ ቢሰሙ ምን አይነት የመንፈስ ቅናት ውስጥ ይዘፈቁ ይሆን!?
እኔ ግን አባባልህን ለቀበለው አልችልም: በባህሪ አልተግባባን ስሜት ፍላጎታችንን አልተፈታተሽን ሚስጥራችንን አልተወያየን... ታዲያ ፍቅር እንደ ህብሰተ- መና ከየት ወረደ?
“አንዱ የሌላውን እገዛ አይዞህ ባይነት ለማግኘት ሲባል የሚደረግ ቀረቤታ ሁሉ ካለአግባቡ በሜዳ የፍቅር ዘውድ ቢጭን
ንጉሥነቱን ማን አምኖ ሊቀበል ይችላል!
“ሶራ አንተ እኔን ስለማፈቅርህ እውን እርግጠኛ ነህ?
“በእርግጥ አንተ ደግ ሩህሩና አሳቢዬ ነህ እንደ
አባቴ የምፈልገውን የልጅነት ፍቅር በመጠኑ ሰጥቶኛል: ያ የአባትና ልጅ ቀረቤታ ግን አልፏል። አሁን የአባቴን ተመሳሳይ ፍቅር
የሚለግሰኝን እጄን ዘርግቼ አልቀበለውም። እንደ እንቁላል ሽፍን ፍቅር አልሻም: አፍርጬ ማየት መቅመስ ማጣጣም እፈልጋለሁ።
“ስለዚህ ከተገናኘን ወዲህ ለአንተ መጠነኛ የሆነ ስሜት አለኝ። ፍቅር ግን አይደለም: አንተን ማጣት ለኔ ትልቅ ውድቀት
ቢሆንም በፍቅር ያልተመሰረተ ግንኙነት ፈጥሬ ልሸሽህ በዚያ ሳቢያ
ልጎዳህና ልጨክንብህ ስለማልፈልግ ስሜቴን እያጠናሁት ነው።
እስከዚያው ግን ግንኙነታችን እንዲለወጥ አልፈልግም:
“ነገ ማታ እደውልልሃለሁ በመጭው ሦስት ቀናት
አልኖርም:: ጓደኛዬን ለመጠየቅና እግረ መንገዴን ለመሰናበት ባርሴሉና እሄዳለሁ... መልካም ጊዜ ለማሳለፍ ሞክር አሁን
መተኛት እፈልጋለሁ ኦርቫ" ብላው ከተቀመጠችበት ተነስታ ወደ መኝታ ክፍሏ ገባች:....
💫ይቀጥላል💫
“አይመስለኝም፤ ቁመናዬን ወደኸዋል። ባህሪዬንና
አስተሳሰቤን ግን ለአንተ ብዙው እንግዳ ነው እና ቢያንስ አትናፍቀውም::
አንተ ከአገርህ ከለመድኸው ባህል ርቀህ ስለመጣህ ብቸኝነትን ይሰማሃል: በአጋጣሚ ደግሞ ብቸኝነትህን የሚቀንስልህ
የሚጋራህና ደስታ የሚፈጥርልህ ሰው ስትፈልግ እኔን አገኘህ። ደስ
አለህ እና እኔን ትፈልገኛለህ እንጂ አታፈቅረኝም: ፍቅር የሚገዛው በህሊና ነው። ወሲባዊ የስሜት ፍላጎት ቢሆን እንኳን በስሜት
ቅፅበታዊ ደስታን ለማግኘት እስከሆነ ድረስ የፍቅር ምልክት ሊሆን
አይችልም::
"...በህይወቴ አፈቀርሁሽ ከመባል ሌላ እሚያስደስተኝ ነገር የሚኖር አይመስለኝም: ጓደኞቼ አንተን አፈቅርሻለሁ ስትለኝ ቢሰሙ ምን አይነት የመንፈስ ቅናት ውስጥ ይዘፈቁ ይሆን!?
እኔ ግን አባባልህን ለቀበለው አልችልም: በባህሪ አልተግባባን ስሜት ፍላጎታችንን አልተፈታተሽን ሚስጥራችንን አልተወያየን... ታዲያ ፍቅር እንደ ህብሰተ- መና ከየት ወረደ?
“አንዱ የሌላውን እገዛ አይዞህ ባይነት ለማግኘት ሲባል የሚደረግ ቀረቤታ ሁሉ ካለአግባቡ በሜዳ የፍቅር ዘውድ ቢጭን
ንጉሥነቱን ማን አምኖ ሊቀበል ይችላል!
“ሶራ አንተ እኔን ስለማፈቅርህ እውን እርግጠኛ ነህ?
“በእርግጥ አንተ ደግ ሩህሩና አሳቢዬ ነህ እንደ
አባቴ የምፈልገውን የልጅነት ፍቅር በመጠኑ ሰጥቶኛል: ያ የአባትና ልጅ ቀረቤታ ግን አልፏል። አሁን የአባቴን ተመሳሳይ ፍቅር
የሚለግሰኝን እጄን ዘርግቼ አልቀበለውም። እንደ እንቁላል ሽፍን ፍቅር አልሻም: አፍርጬ ማየት መቅመስ ማጣጣም እፈልጋለሁ።
“ስለዚህ ከተገናኘን ወዲህ ለአንተ መጠነኛ የሆነ ስሜት አለኝ። ፍቅር ግን አይደለም: አንተን ማጣት ለኔ ትልቅ ውድቀት
ቢሆንም በፍቅር ያልተመሰረተ ግንኙነት ፈጥሬ ልሸሽህ በዚያ ሳቢያ
ልጎዳህና ልጨክንብህ ስለማልፈልግ ስሜቴን እያጠናሁት ነው።
እስከዚያው ግን ግንኙነታችን እንዲለወጥ አልፈልግም:
“ነገ ማታ እደውልልሃለሁ በመጭው ሦስት ቀናት
አልኖርም:: ጓደኛዬን ለመጠየቅና እግረ መንገዴን ለመሰናበት ባርሴሉና እሄዳለሁ... መልካም ጊዜ ለማሳለፍ ሞክር አሁን
መተኛት እፈልጋለሁ ኦርቫ" ብላው ከተቀመጠችበት ተነስታ ወደ መኝታ ክፍሏ ገባች:....
💫ይቀጥላል💫
👍22