አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
573 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ሶስት
:
ደራሲ-በዘረሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...አየሩ ቀዝቃዛ ሲሆን ለሊቱ ደግሞ ፀጥታ ያረበበበት ነው፡፡ምንትዋብ አልጋዋ ላይ ተዘርራ አይኖን ጣሪያ ላይ ሰክታ ታስባለች፡፡ምሽቱም ገፍቶ 7 ሰዓት ማለፉን ግድግዳው ላይ የተንጠጠለውን የወርቅ ቅብ የግድግዳ ሰዓት ይናገራል፡፡እንደ ድሮ ቢሆን ለምንትዋብ ይሄ ጥሩ የእንቅልፍ ሰዓት ነበር ፡፡አሁን ግን ታሪክ ተቀይሯል፡፡ እንቅልፍ ከምንተዋብ መኝታ ቤት ከተሰደደ ሰነባብቷል፡፡
ከመኝታዋ ተነሳች፡፡ ከመኝታ ክፍሏ በመውጠት ከጐኗ ያለውን የልጇን መኝታ ክፍል ተመለከተች እና ስለእሱ አሰበች
‹‹ልጄ ንብረትህን ለበላተኛ አስረከብኩብህ ፡፡ ባክህ ማረኝ፡፡በድዬሀለው ይቅር በለኝ››ስትል ብቸዋን አጉተመተመች፡፡እንባዋን በዓይኖቾ ግጥም አለባት፡፡ከተገተረችበት ተንቀሳቀሰችና እርምጃዋን ቀጠለች፡፡የመስታወት መኝታ ክፍል ገርበብ ብሎል፡፡ በተከፈተው በር አንገቷን አስግጋ ተመለከችና ለደቂቃዎች በገረሜታ አስተዋለቻት..፡፡በሚገርምና በተረጋጋ ሁኔታ ተዘረጋግታ ጭልጥ ባለ ዕንቅልፈ ውስጥ ተውጣለች
‹‹የታደልሽ …ምነው ፈጣሪ ለእኔም ለአንድ ለሊት እንኳን እፎይታ ሰጥተኝ የሰላም እቅልፍ መተኛት በቻልኩ››በማለት ተመኘች፡፡
ለካ አንድ ነገር ሲያጡት ነው ምን ያህል ጠቃሚ እንደሆነ መረዳት የሚችሉት..፡፡በሰላም ተኝቶ..አሪፍ ህልም አልሞ…ታድሶ መነሳት ቀላል እና ተራ ነገር ቢመስልም በዋጋ ሊተመን የማይችል ትልቅ ፀጋ ነው ፡፡ክፋቱ ግን እንዲህ አይነት የሰላም እንቅልፍ እና ጥሩ ህልም በብዙ ሺ ብር የማይገዛ ለሰላማዊ ህይወት የምግብን ያህል አስፈላጊ ነገር መሆኑን ለመረዳት እንዲህ እንደምትዋብ አጥተውት ካዩት ቡኃላ ነው የምር የሚገባው፡፡
ፊቷን አዙራ ወደ ሳሎን በረንዳ ወጣች፡፡ጨላማው ደማቅ ቢሆንም ጨረቃዋ ግን ሙሉ ነበረች፡፡ሙሉነቷ እንደሰዓሊዎች አላስጐመዣትም ፤እንደከዋክብት ተመራማሪዎች አልሳባትም፤በአጠቃላይ ጥሩ ስሜት እንዲፈጠርባት አላደረጋትም ፤እንደውም በተቃራኒው ውስጧ እርብሽብሽ አለባት…መከፋቷ ጠንክሮ የውስጧ ብሶት ከገደቡ አልፎ መንጠባጠብ ጀመረባት..፡፡
‹‹ግን ምን ሀጥያት ሰርቼ ይሆን ..?››ይሄንን ጥያቄ እራሷን ብትጠይቅም መልሱን ግን ከውስጦ ማግኘት አልቻለችም ፡፡ባል ሲሞት ሌላ ባል ማግባት በእሷ አልተጀመረ፡፡እንደማንኛውም ባሎ የሞተባት ሴት የሟች ባሏን አርባ አስቆርባ ፤ሰማንያ ደግሳ አብልታ፤ የሙት አመቱን መታሰቢያ ካከበረች ቡኃላ ነው ለሀዘን ስትለብስ የከረመችውን ጥቁር ልብስ አውልቃ ለሌላ ፍቅር ለሌላ ግንኙነት ዓይኗን የከፈተችው..አጋጣሚ ሆኖ የተከፈተው አይኖ በቅርቧ ያለውን ወርቅ አለማውን ላይ አረፈላት፡፡ አፈቀረችው… አገባችው..፡፡ታዲያ እዚህ ሁሉ ውስጥ የእሷ ጥፋት፤ የእሷ ሀጥያት ምኑላይ ነው …?
በረንዳ ላይ ምን ያህል ጊዜ እንዳሳለፈች ትዝ አይላትም ብቻ ከሀሳቧ ያባነናት ከውስጥ የሰማችው የበራፍ መከፈት እና መዘጋት ድምጽ ነው፡፡
‹‹ማነው? ››በማለት ተንቀሳቀሳ የሳሎኑን በራፉ ከፈተችና ወደ ውስጥ ገባች..ምንም አይነት እንቅስቀቃሴ አይታያትም፡፡የራሷን ጆሮ ተጠራጠረች..‹‹‹እያበድኩ ይሆን እንዴ?››እራሷን ጠየቀች፡፡በዝግታ እርምጃ ወደ መስታወት መኝታ ክፍል አመራች፡፡ክፍሏ እንደቅድሙ ገርበብ እንዳለ ነው፡፡ወደውጥ አንገቷን አስግጋ ተመለከተች …ከእንደ ቅድሙ የተዘረጋጋ የመስታወት አካል ግን አልጋው ላይ አይታይም ..የተዘበራረቀ ብርድ ልብስና አንሶላ እለዩ ላይ የተከመረት ባዶ አልጋ ብቻ….
‹‹ድምጽ መስማቴ ቅዠት አልነበረም ማለት ነው..መቼስ ፊኛዋ አይቋጥር.. ወደሽንት ቤት ሄዳ ይሆናል›› ስትል አሰበች፡፡ወደበረንዳዋ ልትመለሰ ፊቷን ስታዞር አሁንም ጆሮዋ ውስጥ የሆነ በዚህ ሰዓት መሰማት የሌለበት ድምጽ ጥልቅ አለባት፡፡ የሰው ድምፅ..ንግግር የመሰለ ድምጽ..ትኩረቷን ወደእዛ ላከች..ድምጹ ከልጇ መኝተ ክፍል አካባቢ የሚበተን መስላት፡፡..በመገረም ወደእዛው አመራች፡፡በደንብ ተጠጋችና ጆሮዋን ግድግዳው ላይ ለጥፋ ማድመጥ ጀመረች፡፡የወንድ እና የሴት ንግግር ነው፡፡
‹‹ለምን አትሰሚኝም ጥያቄሽን ልቀበል አይቻለኝም››
የልጇ ድምጽ ነው፡፡‹‹ወይ ጉድ በዚህን ሰዓት የምን ጥያቄ ይሆን…?››ምንትዋብ በውስጧ አብሰለሰለች፡፡ ከውስጥ የሚሰማው ንግግር ቀጥሏል
‹‹አውቃለው ብዙ ጊዜ ነግረኸኛል››
‹‹እናስ?››
‹‹እናማ የምትለው አይገባኝም….የቤታችሁ ሰራተኛ ብሆንም አንተን ከማፍቀር እራሴን ማቀብ አልተቻለኝም››
‹‹መስታወት አሁን ተረጋጊና ወደክፍልሽ ተመለሺ…ባይሆን ነገ በቀኑ እንነጋገራበታለን››
‹‹እንደዚህ ብለህ እኮ መአት ቀን አታለኸኛል፡፡››
‹‹ወድጄ አይደለም እኮ ታውቂያለሽ በጣም የምወዳት ፍቅረኛ አለቺኝ ፡፡ፈጽሞ እሷን ማጣት ስለማልፈልግ ከሌላ ከማንኛውም ሰው ጋር በፍቅር መነካካት አልፈልግም››
‹‹ያነው ትክክለኛ ምክንያትህ ወይስ የቤት ሰረተኛ በመሆኔ ደበርኩህ?››
‹‹መስታወት እኔ እኮ አንቺን እንደ እህቴ እንጂ እንደቤት ሰራተኛ አይቼሽ አላውቅም፤ እዚህ ቤት እንደ እህት እና ወንድም አብረን ነው ያደግነው..ሰራተኛ መሆንሽን አንቺ ስትነግሪኝ ብቻ ነው ትዝ የሚለኝ ..››
‹‹ውሳኔህ ግን ፍትሀዊ አይደለም››
‹‹እንዴት… ?ፍትህና ፍቅርን ደግሞ ምን አገናኛቸው…በፍቅር ውስጥ ፍትህ ቦታ የለውም…አንቺ የጫማሽ ሶል ተሰንጥቆ ውሀ እያስገባ ለምትወጂው ሰው ግን ተበድረሽ ጃኬት ገዝተሸ ልትሰጪው ትቺያለሽ?...ፍቅረኛሽ በሆነ አሸባሪ እጅ ገብቶ እጁ ከሚቆረጥ አንቺ አንገትሽን ሰጥተሸ መሞትን ትመርጪያለሽ…..ወይም የምትወጂው ሰው በሽታ ተይዞ ሆስፒታል ቢገባ እና እሱን የምታሳክሚበት ገንዘብ ብታጪ ወይም ሌላ አማራጭ ባይኖርሽ ሸርሙጠሸም ሆነ ብር ከሚሰጥሽ ወንድ ጋር ተኝተሸ የእሱን ህክምና በመክፈል ልታሳክሚውና ልታድኚው ትችያለሽ..ታዲያ እነዚህ በምሳሌ ከጠቀስኩልሽ ክስተቶች መካከል የትኛው ነው ፍትሀዊ የሚባለው… ?አየሽ በፍቅር ውስጥ ፍትህ ታናሽ ነች…ለዚህ ነው በፍቅር እና ጦርነት ውስጥ ሁሉ ነገር ትክክል ነው የሚባለው… ስለዚህ እኔም በሮዝ ላይ ያለኝ አቋም በፍቅር የተቃኘ ስለሆነ ትክክል አይደለህም ልትይኝ አትቺይም›
‹‹ቢሆንም…ለማታፈቅርህ.. ለአንተ ቅንጣት ደነታ ለሌላት ሴት ስትል የምታፈቅርህን ሴት መግፋት..ቢያንስ እሺ አታግባኝ ..ወይንም እንደፍቅረኛህ አትቁጠረኝ..ግን ቢያንስ በድብቅም ቢሆን ከፍቅርህ እንድቋደስና እቅፍህ ውስጥ እንድገባ ብትፈቅድልኝ ነፍሴ ትደሰት ነበር ..ማምሻም እኮ ዕድሜ ነው..››
‹‹አይ መስታወት ፍቅር ፍቅር ነው…አብሬሽ ምተኛው ሳቅርሽና ስታፈቅሪኝ ብቻ ነው››
‹‹ባክህ ዝም በል፤ይሄ ህግ እኔ ላይ ሲሆን ብቻ ነው የሚሰራው..ከማታፈቅርህ ጋር ትኖር የለ..››አንቧረቀችበት፡፡
ምንትዋብ ከዚህ በላይ መታገስ አልቻለችም..በራፍን በርግዳ ወደ ልጇ ክፍል ዘው ብላ ገባች፡፡መሀሪ ከተቀመጠበት የአልጋ ጠርዝ መስታወት ከተቀመጠችበት ወንበር ሁለቱም ተስፈንጥረው ተነሱና ቆሙ፡፡ ያልጠበቁት ስለሆነ ሁለቱም በእፍረት አንገታቸውን ወደምድር አቀረቀሩ ምንትዋብም ሁለቱንም እያፈራረቀች ለደቂቃ ያህል በፅሞና ከተመለከተቻቸው ቡኃላ
‹‹መኝታ ቤት መጋራት ከጀመራችሁ ቆየ እንዴ?››የአሽሙር ንግግሯን ተናገረች መልስ ሚሰጣት ስታጣ ቀጠለች
‹‹አንቺ ለካ ስራ ብዙ ነሽ ቀን በጉልበት ስራ ስትባክኚ ትውያለሽ ለሊት ደግሞ እዚ……አሁን ጨርሰሻል ወይስ እዚሁ ነው የምታድሪው?››መስታወት ምንም ሳትናገር ሹክክ ብላ ክፍሉን ለቃ ወደራሷ ክፍል አመራች፡፡መሀሪ ግን እንደተገተረ ነው ምንም እንኳን እራሱን የቻለ ለአቅመ
2👍2
አዳም ከደረሰ አመታተን ያስቆጠረ ቢሆንም በዚህ ጉዳይ እናቱን ብዙም አይደፋራትም፡፡ምንዋብም በቆመችበት በልጇ ላይ ብታፈጥበትም ምን መናገር እንደለባት ግራ ገባት…ደግሞ ልጇን አጥፍተሀል ብሎ ለመቆጣት ምን የሞራል ብቃት አላት ?
‹‹በል ድህና እደር ››ብላ ከክፍሉ ለመውጣት ፈቷን አዙር ስትንቀሳቀስ ሳሎን ያለው ስልክ ተንጫረረ..ፍጥነቷን ጨምራ ወደ እዛው አመራች..
ኩማንደር መሀሪም ግራ ተጋባና ሰዓቱን ተመለከተ 7፤45 ይላል ፡፡‹‹በዚህ ሰዓት ማነው የሚደውለው?ያ ዕብድ ደረሰ እንዳይሆን ብቻ..?መቼስ እሱ ከሆነ በእዚህ ሰዓት ጥንብዝ ብሎ ሰክሮ መሆን አለበት..››ተጨነቀ
‹‹በስካር መንፈስ ዘባርቆ ጭራሽ ነገሮችን እንዳያባብስ ሰጋት ቀስፎ ያዘው ..እናቱን ተከትሎ ወደሳሎን ተንቀሰቀሰ ፡፡
//////
እናቱ ስልኩን አንስታ ማናገር ጀምራች
‹‹ለመሆኑ ነፍስህ አለ?››
‹‹መኖር ከተባለ?››
‹‹እንዴት ምን አጋጠመህ...?ለመሆኑ የት ነው ያለኸው ....?ደግሞ ሰው ያስባል አትልም እንዴ?››ግትልትል ጥያቄዎችን በአንዴ ደረደረችለት፡፡
ቀለም ወርቅ በተረጋጋ እና ለስለስ ባለ ድምጸት ከዛኛው የስልክ ጫፍ የሚያወራው ይሰማዋል‹‹ቀስ በይ እንጂ..እዬዬም ሲዳላ ነው ሲባል አልሰማሽም..ያልሻቸውን ነገረች ሁሉ ለማድረግ እኮ ማድረግ የምችልበት ሁኔታ ላይ መሆን አለብኝ››
በምንትዋብ አዕምሮ ውስጥ ለወራት የዘለቀው ስጋት እውን መሆኚያው ደቂቃ መቅረብን ሰውነቷ ነገራት…
‹‹የሆንከውን ልትነግረኝ ትችላለህ?››አለችው ተስፋ በመቁረጥ ጫፍ ላይ ባለ ስሜት
‹‹ መደወሌ እኮ የሆንኩትን ልነግርሽ ነው….››የምንትዋብ ሰውነት ሲንቀጠቀጥን የስልኩን እጄታ መያዝ አቅቷት ስትቸገር ከዛ እልፎ ለመውደቅ ስትንገዳገድ ልጇ መሀሪ በቅርብ እርቀት ሆኖ እየተመለከተ ነው፡፡እንደጠረጠረው ሰልኩን የደወለው ጓዳኛው ደረሰ ሳይሆን ያልጠቀው ቀለመወርቅ መሆኑ አስገርሞታል … አስፈርቶታልም፡፡
‹‹እሺ ንገረኝ..እያዳመጥኩህ ነው››
‹‹በደንብ አድምጪኝ አሁን ያለውት ሱዳን ነው፡፡በድንገት ቆንጇ ስራ አለ ብለውኝ ደላሎች አጭበርብረውኝ የንግድ ዕቃ ጭኜ ወደ ደቡብ ሱዳን ጁባ ነበር ያመረውት..፡፡እንደተባለውም ይዤ የሄኩትን ዕቃ እጥፍ በሆነ ትርፍ መሸጥ ችዬ ነበር፤ ግን ምን ዋጋ አለው ብሩን በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ብድኖች ድንገት ወረሩንና ደብድበውና ቀጥቅጠው ዘረፍኝ ..አሁን ባዶዬን አስቀርተውኛል፡፡ኤፍ.ኤስ.አር መኪናችንንም አቃጠሏት፡፡ ባዶዬን ቀርቼያለው..ይሄውልሽ…››
/////
የስልኩ እጄታ ከእጆ ተንሸራቶ ወደ መሬት ተምዘገዘገ ፡፡እሷም በአንድ ወገን ዘንበል ብላ ልትገነደስ ስትል ሁኔውን በተጠንቀቅ ቆሞ ሲከታተል የነበረው ልጇ ፈጠን ብሎ ደረሰላተትና ደጋግፎ ወደመኝታ ክፍሏ ወሰዳት፡፡
በዚህ ሰዓት በዚህ ሁኔታ ላይ ሆኖ የወሬውን ዝርዝር ሊጠይቃት አልፈለገም፡፡ ያንን ማድረግ ይበልጥ እንድትጨነቅ እና እንዳትረጋጋ ማድረግ ነው ብሎ ስላሰበ ተወው፡ከእዛ ይልቅ እንቅልፍ እንዲወስዳት አመቻችቶ አስተኛትና ክፍሉን መለስ አድርጐላት ወደ መኝታ ክፍሉ ተመለሶ ትካዜ ውስጥ ገባ፡፡እስከአሁን በቤቱ ነግሶ ከነበረው ጭንቀት ይልቅ በቀጣቹ ቀኖች የሚከሰተው ሁኔታ ጨለማ እንደሚሆን ሲታሰበው በሰውነቱን ቅጽበታዊ ቅዝቃዜ ተሰራጨ….ልቡ ድረስ የተሰማው ኩምትርትር የሚያደርግ ቅዝቃዜ….

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
1👍1
#እናቴ_ትሙት_አንላቀቅም !

1⃣

“ሰማህ የኔ ውድ . . .
ሳፈቅርህ ከልቤ ባንተ ተረትቼ
ስላንተው ስባክን አቅሌን ነፍሴን
ስቼ
በክንድህ እያሟሟህ ባፍህ
እያቀለጥከኝ
ከማያውቁት ዓለም ወስደህ
እየከተትከኝ
ነፍሴን አስክረሃት በሀሴት ዳንኪራ
እንዳልቆም እንዳልሄድ ያላንተ
እንዳልሰራ
አድርገህ ጠንርፍህ እንዲህ አሳስረኸኝ
እሄዳለሁ ብትል ከመንገድ ጥለኸኝ
እናቴ ትሙት አንላቀቅም
እኔ በፍቅር ቀልድ አላውቅም!”
ስትይኝ ፈራለሁ
አንዳንዴም ኮራለሁ
አንዴ ደስ ይለኛል
አንዳንዴ ይጨንቀኛል።
👇
👍2
#እናቴ_ትሙት_አንላቀቅም

2⃣

“እየውልህ ውዴ . . .
እኔማ ስወድህ ሁኚ ያልከኝን ሆኜ
የኔን ዓለም ትቼ ባንተ ዓለም
መንኜ
ጠቅልዬ ግብቼ ከገዳምህ ዋሻ
በስምህ ፀልዬ ሃጢያቴን ማስረሻ
እንደሆነ መቼም አንተም
ታውቀዋለህ
ከቶ ያልሰጠውህ ኧረ እንደው ምን
አለህ
ታዲያ ሁሉን ወስደህ ባዶዬን ቀርቼ
ኑሮዬን በሞላ አንተው ላይ ገንብቼ
ስታውቀው እንዳልኖር አንተን
ተለይቼ
እሄዳለሁ ብትል ድንገት አንቺን ትቼ
እናቴ ትሙት አንላቀቅም
እኔ በህወት ቀልድ አላውቅም!”
ስትይኝ ፈራለሁ
አንዳንዴም ኮራለሁ
አንዴ ደስ ይለኛል
አንዳንዴ ይጨንቀኛል።
👇
#እናቴ_ትሙት_አንላቀቅም

3⃣

ሰማሽ የኔ እመቤት . . .
እውነት አንቺን ርቄ
እምነትሽን ፍቄ
በፍቅርሽ ቀልጄ
ሌላ ሴት ለምጄ
ምኖር ይመስልሻል ?!
እውነት እውነት እውነት
በእውነት ተሳስተሻል !
ደግሞ ፉከራሽን ዛቻሽን ፈርቼ
እንዳይመስልሽ ውዴ እኔስ ተረትቼ!
ይልቅ እኔም አልኩሽ . . .
እናቴ ትሙት አንላቀቅም
ካንቺስ ወዲያ ሴት አላውቅም።

🔘አብዲ ሰዒድ🔘
👍1
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_አራት
:
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...ቁርስ መብላት ትቶ እየቆነጠረ ሲተክዝ ታዝባው ግራ በመጋባት‹‹ቁርስህን በልተህ ወደስራ አትሄድም እንዴ ?እየረፈደብህ እኮ ነው››አለችው መስታወት
‹‹ምኑን ሄድኩት ››አላት ከትካዜው ::
‹‹እንዴት? ምነው የማታው ነገር አሳሰበህ እንዴ?አይዞህ እንኳን አንተ እኔም አልተጨነቅኩ፡፡እርምጃ ቢወሰድም እኔ ላይ ነው፡፡ ከቤቱ ብባረርም እኔው ነኝ..ያ ከሆነ ደግሞ ላንተ ይበልጥ ጥሩ ይሆናል …ከእኔ የዘወትር ጭቅጭቅ ትገላገላለህ››
‹‹አይ… ዶሮ ብታልም ጥሬዋን….መች ይሄ አሰሰበኝ ብለሽ ነው››አላት..እውነቱን ነወ..ውስጡ የፍርሀት ቆፈን ጨረማምቶታል…ከመቼውም በላይ ነገን እየፈራ ነው….የእናቱ ጤንነት ስጋት አሳስቦታል..
‹‹ታዲያ ምን አዲስ ነገር ተከስቶ ነው እንዲህ ፊትህን የሆረር ፊልም አክተር ያስመሰልከው?››
‹‹ባክሽ ሊሊት ሰውዬው ደውሎ ነበር››
‹‹የቱ ሰውዬ?››
‹‹ወርቅአለማው ነዋ.. ሌላ ምን ሰውዬ አለ?››
‹‹ ….ምን ሆኜ ጠፋው አለ?››
‹‹ባክሽ ያለውን ነገር አላውቅም፡፡ ግን ጥሩ ዜና ያበሰራት አልመሰለኝ፡፡ ፍጽም ተስፋ ቆርጣ ና አቅመ ቢስ ሆን ነበር ለሊት ወደ መኝታዋ ያመራችው..››
‹‹ታዲያ እንዴት እንዳደረች አላየሀትም?››
‹‹አይ አላየዋትም፡፡ ሰሞኑን ያጣችውን እንቅልፍ ምን አልባት ዛሬ አግኝታ ከሆነ እንዳልረብሻት ስለፈራው ነው››
መስታወት በለበሰችው ቀለም የበዛበት ቀሚስ ላይ ደርባ ያገለደምችውን ነጭ ሽርጥ ላይ እጇን እየጠራረገች‹‹ቆይ እስቲ ቀስ ብዬ አይቼት ልምጣ ››ብላ ወደ ምንትዋብ መኝታ ቤት በመንሾከክ ሄደች…. ቀስ ብላ በራፉን ገፋ አደረገች ፡፡ከውስጥ ስላልተቀረቀረ በቀላሉ ተከፈተላት፡፡የማታው ትዕይንት በአዕምሮዋ መጣባትና ፈራች
‹‹…ያንን አስታውሳ ትቆጣኝ ይሆን? እንደፍጥርጥሯ ፡፡መጋፈጥ እንጂ ሸሽቼ ማመልጠው ጉዳይ አይደለም ›› በማለት እራሷን አበረታታችና ወደውስጥ ገብታ አይኖቾን ወደአልጋው ወረወረች፡፡ምንትዋብ ዝርግትግት ብላ አልጋው ላይ ተዘርራ ትታያለች፡፡እንቅልፋ አልወሰዳትም፡፡ አይኖቾ ይንከባለላሉ፡፡
‹‹ምንቴ ደህና አደርሽ?››
ፈራ ተባ እያለች ጠየቀች፡፡መልስ አልሰጠቻትም፡፡‹‹በለሊቱ ድርጊቴ ተቀይማኛለች ማለት ነው…›› ስትል አሰበች፡፡በዚህም በውስጧ ሲጉላላ የነበረው ስጋቷ ናረባት…
‹‹ምንቴ በማታው ጉዳይ ተቀይመሺኝ ከሆነ ይቅርታ ሁለተኛ አይደገምም..››አሁንም መልስ የለም ..ግን ከሁለቱም አይኖቾ እንባ መንጭቶ መንኳለል ጀምሯል፡፡
መስታወት ይበልጥ ደነገጠችና በጣም ተጠግታት አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ አለች‹‹ ምንቴ አረ ተረጋጊ ..ነገሮች እኮ እንዲህ እንደተበለሻሹ አይቆዩም… በሂደት ይስተካከላሉ››
‹‹ምንቴ ኸረ በፈጣሪ አታልቅሺ እጆን ወደ ጉንጮ ላከችና አንባዋን ታብስላት ጀመር፡፡ ከምንትዋብ በኩል ግን ለውጥ አልነበረም፡፡
መስታወት ግራ ተጋባች‹‹ምንቴ…››መልስ የለም››ብርድልብሱን ገለጠች፡፡ቢጃማ ለብሳለች እጆን ያዘችው እንደተንከረፈፈ ነው..በአየር ላይ እንዳለ ስትለቀው እንደተዘረጋጋ ወደቦታ በራሱ ተመለሰ..እግሯንም ብድግ እንደማድረግ አለችና ስትለቀው ተመሳሳይ ነው ፡፡ምንትዋብ ሰውነቷን በአዕምሮዋ ማዘዝ አትችልም፡፡መስታወት ድንገት ሳታስበው ጩኸቷን ለቀቀችው…በሰከንድ ውስጥ መሀሪ የመኝታ ቤቱን በራፍ በርግዶ ገባ
‹‹ምንድነው? ምንሆንሽ?››
‹‹አትናገርም..እጅና እግሯንም ማዘዝ አትችልም››በተረዳችው መጠን ልታስረዳው ሞከረች፡፡
‹‹እንዴት ሆኖ ..?እማ ..እማዬ ምን ሆንሽ?››እጁን በአንገቷ ዙሪያ ሰቅስቆ በመክተት እየነቀነቃት ቢጠይቃትም አሁንም እንባ ከማፍሰስ ውጭ ምንም ልትለው አልቻለችም››
‹‹ወይኔ እናቴ !! ወይኔ ጉድ ሆንኩ!!››ብር እየተርበተበተ መልሶ አስተኛትና ስልኩን አውጥቶ ደወለ፡፡ ባለመኪና የሆነ ጐረቤቱ ጋር ነው የደወለው ..መኪና ይዞ እንዲመጣለት
‹‹በይ እስኪመጣ ልብስ አምጪ እንቀይርላት፡፡››መስታወት እየተርበተበተች ወደ ቁም ሳጥኑ ሄደች፡፡ ልብስ መርጣ አመጣችና በመከራ እየተጋገዙ የለበሰችውን ልብስ አወለቁላትና ሌላ ልብስ አለበሶት፡፡ አዕምሮዋ ሙሉ በሙሉ አካሏን የማዘዝ ስልጣኑን ሙሉ በሙሉ ተነጥቆል፡፡
መሀሪ የእናቱ የሰሞኑ ሁኔታዋ በጣም ሲያሳስበው የቆየ ቢሆንም እዚህ ደረጃ ደርሶ በጤናዋ ላይ አደጋ ያመጣባታል ብሎ ፈጽሞ ተጠራጥሮ አያውቅም ነበር፡፡ይሄ የሚያሳየው ደግሞ የቀለም ወርቅ ጉዳይ ምን ያህል የእናቱን ልብ እንደሰባበረው ነው፡፡
አሁን ደግሞ የእሱም ልብ መቃጠል ጀምሯል፡፡ውስጡ በንዴት እየተንበለበለ ነው፡፡እንዴት አድርጐ አግኝቶ በእንዴት አይነት ሁኔታ ሊበቀለው እንደሚችል ለጊዜው ባይገለጽለትም ግን እንደዛ ማድረጉ እደማይቀር እርግጠኛ ነው፡፡
የተደወለለት ሰውዬ መኪናውን ይዞ መጣና አፋፍሰው ተሸክመው አስገብተዋት ወደ ሆሰፒታል ይዘዋት ሄዱ ፡፡እንደ ደረሱ ከመኪናው ወደ እስትሬቸሩ አሸጋገሯት እና ወደ ምርመራ ክፍል ይዘዋት ሲገቡ መስታወት ደግሞ ስልኳን አውጥታ መደወል ጀመረች
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
‹‹ሄሎ..መስታወት ››የመዝናናት ስሜት የተጫነው ሞዛዛ ድምጽ
‹‹ሄሎ ሮዛ አሁኑኑ ሆስፒታል ድረስ መምጣት ትቺያለሽ ?››
‹‹ታሾፊያለሽ..ምን ተፈጠረ?››
‹‹ባክሽ አትቀልጂ መሀሪ ችግር ላይ ነው ››
‹‹የምን ችግር..?ወንጀለኛ ተኩሶ አቆሰለው እንዴ…?ሞተ ማለት ነው?››
መስታወት ምነው ባልደወልኩላት ብላ ተፀፀተች..‹‹ቢሞትም በቃ እንዲህ ነው ተንቀባራ የምትሰማኝ…ይህቺን ታህል ብቻ ነው ድንጋጤዋ….ምን አይነት ልበ ደንዳናነት ነው…ስትል ገረሜታዎን በውስጦ አብሰለሰለች፡፡
‹‹ባክሽ እናቱ በጣም ታማ ነው ከቻልሽ ለኩማደር ጓደኛውም ደውለሽ ንገሪው..››
‹‹ወይኔ አማቼ በቃ ሰርጌን ልታሰናክል ነው እንዴ!! ››አሾፈች
‹እንግዲህ ትመጪ እደሆን ነይ ካለበለዚ የራስሽ ጉዳይ››አለቻትና ሞባይሉን ጆሮዋ ላይ ጠረቀመችባት፡፡
መስታወት በሁኔታዋ በጣም ተበሳጭታለች‹‹አሁን ሰው ይህቺ ፍቀረኛዬ ነች ብሎ አብሮ ይኖራል..?የታባቱ ይበለው››አለችና ሆስፒታሉ ኮሪደር ላይ ባለው አግዳሚ ላይ ተቀመጠች፡፡መሀሪ በቅርብ ርቀት ወዲህ ወዲያ እያለ በጭንቀት ሲሰቃይ እየተመለከተችው ነው፡፡ ያም ጨክና እንድትጨክንበት ሊያደርጋት አልቻለም….ውስጦ ተንሰፈሰፈበት……
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ለመሀሪ ይህ ወቅት በህይወቱ በጣም መራሩ ወቅት ሆኖበታል፡፡ወላጅ እናት ስትከፋ ማየት ውስጥን ያሳዝናል..ወላጅ እናት ታማ አልጋ ላይ ወድቃ ማየት ደግሞ ውስጥን ያሳምማል፡፡ስለዚህ የእሱ ውስጥም በዚህ ሰዓት በጣም ታሟል፡፡በልጅነቱ ‹‹እሹሩሩ…ማሙሽ እሹሩሩ..
ማሙሽ እሹሩሩ
ልጄ እሹሩሩ…
ስወቅጥም አዝዬ ..
ስፈጭም አዝዬ…
ወገቤን አመመኝ ና ውረድ ማሙዬ…
ብለው ሲያባብሉት፤አባብለውም ሲያስተኙት የነበረው የእናቱ አንደበት ተቆልፎል፡፡ሰውነቱን በፍቅር እየዳበሱ ያሳደጉት የእናቱ አለንጋ ጣቶች ዛሬ አቅም አንሷቸው ዝርግትግት ብለዋል…ከእዚህ እዛ እየኳተኑ ..ከቦታ ቦታ እየባከኑ ሚያስፈልገውን ነገር ያቀርቡለት የነበሩት የእናቱ እግሮች ዛሬ ድንገት አቅም አልባ ሆነው አልጋው ላይ ተዘረጋግተዋል..ታዲያ ለአንድ ሰው ከዚህ በላይ የሚያም .. ከዚህ በላይ የሚከብድ መከራ ከየት ይመጣል ……ፈራ ..ነገን በጣም ፈራ፡፡ጥልቅ ድረስ እስኪሰማው እና እስኪንቀጠቀጥ ድረስ ፈራ…..
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ሮዝ የመሀሪ እናት ሆስፒታል መግባቷን መስታወት በስልክ ደውላ ስትነግራት አልጋዋ ውስጥ ነበረች፡፡

‹‹ሲደብር ይህቺ ደባሪ አሮጊት ደግሞ ካልጠፋ ቀን በዛሬ ቀን ትታመማለች እንዴ›
👍6
ስትል ተማረረች፡፡ዛሬ ቀጠሮ ነበረባት ፡፡ሶስት ጓደኛሞች የሆኑ ወጣቶች ሊያዝናኖት ከ7 ሰዓት ጀመሮ ፕሮግራም አስይዘዋት ነበር፡፡እነዚህ ልጆች ከዚህ በፊትም ሶስት አራት ጊዜ በተመሳሳይ ሁኔታ አዝናንተዋት ያውቃሉ፡፡ከእነሱ ጋር ስትውል ነፍሷ ሀሴት ነው ምታደርገው፡፡ እስክትግል ድረስ ያስቅሟታል..እስክትንገዳገድ ያጠጧታል..ከዛ ይዘዋት ያድራሉ….፡፡‹‹ለስንት ?››እንዳትሉ፡፡እነዚህን ልጆች የምትወዳቸው አንደኛው በአንደኛው ሳይቀና ..ተሳስበውና ተግባብተው አብረው ስለሚቋደሷት ነው፡፡ ብትንትን እስክትል ተጋግዘው ስለሚያስደስቷት ነው፡፡የግሩፕ ወሲብ ላይ መሳተፍ ..ወይም በግሩፕ የተደራጁ ወንዶችን በወሲብ ማስተናገድ ለሮዝ አዲስ ነገር አይደለም ከ17ዓመቷ ጀመሮ ደገጋግማ ያደረገችውና በጣም የምትደሰትበት ነገር ነው፡፡ለዚህ ነው አሁን የተበሳጨችው፡፡ ይህን የመሰለ አስደሳች ነገር ችላ ብላ ሆስፒታል ከበሽተኛ ጋር ማሳለፉን ስታስበው ነው የደበራት፡፡እንደምንም ተነስታ ፊቷን ታጥባ ልብሷን ለባብሳ፤ ተኮኩላ ና ተቀባብታ ከቤቷ እስክትወጣ 35 ደቂቃዎች ፈጅቶባታል፡፡የኩማደሩ ስልክ እምቢ ስላላት ቀጥታ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ነው ያመራችው፡፡
አለባበሷን ያስተዋለችው ከቤቷ ወጥታ ታክሲ ተሳፍራ ስትቀመጥ ከጐኗ የነበረው አንድ ጐረምሳ ከሰጣት አስተያየት በመነሳት ነው፡፡
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
‹‹ኸረ አሁንስ ለእናንተ ስንል ወዴት እንሂድ?››ነበር ያላት
‹‹አቤት››ኮስተርተር አለችበት፡፡
‹‹እንዲህ እያማራችሁ በዛ ላይ ግምሽ ዕርቃን ሆናችሁ ሚስጥራዊ አካላችሁን ሳይቀር ለእይታ እያጋለጣችሁ .. እኛ እንዴት እንሁን..?ለፍቅረኞቻችንስ እንዴት እንታመን….?››
‹‹ይህቺ ጠጋ ጠጋ ዕቃ ለማንሳት እንዳይሆን?››
‹‹ፊት ለፊት ያለ ዕቃ ቢነሳ ምን ያስደንቃል?››
‹‹እየተሳደብክ ነው እንዴ?››
‹‹በፍጹም አይደለም… ደግሞ ለምንድነው ፓንት ያላደረግሺው?››አመዷ ቡን አለ፡፡ቆንጣላ ጉርድ ቀሚሷን ወደ ታች ለመጐተት ጥረት ብታደርግም አልተሳካላትም
‹‹አይ…!!!ልትሸፍኚው እየሞከርሽ ነው?›› ብሎ ጭራሽ አሳፈራት፡፡
‹‹ዝም ብለህ በግምት ባትናገር ጥሩ ነው …መስሎህ ነው እንጂ አድርጌያለው››አለችው በሹክሹክታ ወደ ጆሮው ጠጋ ብላ፡፡
‹‹ማድረግማ አድርገሻል፡፡ ሮዝ ቀለም ያለው አይደል.. የገረመኝ ግን ቀሚስሽም ብጣቂ ..ፓንትሽም ብጣቂ መሆኑ ነው››
‹‹የሆንክ ቡዳ ነገር ነህ …ለመሆን ፓንቴን እንዴት አድርገህ አየኸው?››
‹‹ታክሲ ውስጥ እንደገባሽ ለመስተካከል እግርሽን ወዲህ ወዲያ ስታደጊው ጓዲያሽ ውስጥ ያሉት ነገሮችሽ ሳላስበው አይኔ ውስጥ ገቡ…››አላት ፈገግ እያለ፡፡
ንግግሩም እይታውም ሰውነቷ እንዲግል አደረጋት፡፡በተቀመጠችበት ተቁነጠነጠች፡፡
‹‹‹ምነው ዝም አልሽ?››
‹‹ምን ልበልህ? ፈራውህ እኮ››
‹‹አይዞሽ ያንቺን ያህል አስፈሪ አይደለውም..በነገራችን ላይ ዳንኤል እባላለው፡፡››
‹‹እኔ ደግሞ ሮዛ››
‹‹ስምን መላአክ ያወጣዋል ማለት እንዲህ ነው..መልክሽን ሲያስተውሉት ከዓይን ሞልቶ ይፈሳል..ስምሽንም ሲጠሩት አንደበት ውስጥ ይደምቃል››
‹‹አመሰግናለው››አለችው ያለወትሮዋ እየተሸኮረመመች፡፡
‹‹ምስጋናው ቀርቶብኝ …ሞባይል ቁጥርሽን ብታውሺኝ››
አልተግደረደረችም፡፡ መውረጃው ቦታ ስለደረሰች በፍጥነት ነገረችውና ተሰናብታው ታክሲውን አስቁማ ወረደች፡፡እሱም በዓይኖቹ ሸኛት፡፡ከኋላዋ እያያት እንደሆነ ገብቶታል፡፡ይሄ ልዩ ተሰጥኦዋ ነው፡፡ ምን ግዜም ከኃላዋ የወንድ ዓይን ከተሰካባት ጀርባዋን ይሞቃታል..፡፡ይሄ ሁኔታ ሁሌ ይገርማታል…….
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ፖሊስ ጣቢያ ግቢ ውስጥ ገባችና ወደ ኮማንደር ደረሰ ቢሮ አመራች፡፡ስታንኳኳ
‹‹ይግቡ›› የሚል ድምጽ ከውስጥ ስለሰማች በሩን ገፋ አድረጋ እግሯን አስቀድማ ገባች
‹‹የተከበሩ ኩማንደር እንደምን አደሩ?››
‹‹አንቺው ነሽ እንዴ እንዲህ መላአክ መስለሽ በጥዋት የምታስደነግጪኝ?››ሲላት ታክሲው ውስጥ ባገኘችው ወጣት ቀስቃሽነት ይዛ የመጣችው ሙቀት ይበልጥ በመላ ሰውነቷ ተሰራጭቶ አቅነዘነዛት፡፡
‹‹እኔ በመሆኔ ከፋህ እንዴ?››
‹‹ባይከፋኝም አልዋሽሽም… የጓደኛዬ ሚስት ባትሆኚ ይሻለኝ ነበር?››
‹‹ባልሆን ምን ታደርገኝ ነበር…?››ጠየቀችው..በመንሰፍሰፍ፡፡
‹‹ያው በዚህ ብርሀናማ ጥዋት ከአንድ አማላይ ወጣት ሴት ጋር ምን ማድረግ የምፈልግ ይመስልሻል?››
‹‹ልገምት?››
‹‹ገምቺ››
‹‹ወደ ኃላዋ ተመለሰች እና የቢሮውን በራፍ ከውጥ ቀረቀረችውና ..ልብሷን ከላይ ጀምራ እያወለቀች ወደ እሱ መሳብ ጀመረች፡፡ ኩማንደሩ ደነገጠ፡፡ ግራ ተጋባ ፡፡ማሰቢያ ጊዜ ግን አላገኘም….የጓደኛው እጮኛ የሆነችው ይህቺ አማላይ ሰይጣን ዕርቃኖን ጠረጴዛው ላይ ወጥታ የእሱን ልብስ ለማውለቅ ትረዳው ጀመራለች፡፡እሱም በፍጥነት ተባበራት..፡፡አዎ አሁን የሚደረገውን አድርጐ ቡኃላ ቢያስብበት ይሻለዋል፡፡ በቅጽበት አውሬ ሆነችበት….ተጠመጠመችበት..ሳመችው… ነከሰችው… ቧጨረችው፡፡ ነፍሱ ጥፍት አለችበት፡፡ ቢሮ በደቂቃ ውስጥ ተተረማመሰ ፡፡በህይወቱ አይቷት የማያውቀው የወሲብ አለም ውስጥ ከታ አሳሩን አበላችው፡፡ የመጨረሻ ጡዘት ላይ እኩል ደርሰው እኩል ነው የረገቡት..፡፡
ነገሮች ከተጠናቀቁ ቡኃላ ግን የሮዝ የሚያስደነግጥ ተንሰቅሳቂ ለቅሶ ነበር የተከተለው፡፡ኩማንደሩ በጣም ደነገጠ..፡፡በሁኔታዋ ግራ ገባው፡፡ ልብሱን እንደነገሩ በፍጥነት ለበሰና ወደእሷ ተጠጋ‹‹እንዴ ምን ያስለቅስሻል? አስገድጄሽ እኮ አይደለም? ሁለታችንም በፍቃደኝነት ፈልገነው ነው ያደረግነው፡፡››
ልብሷን ከተበታነበት ወለል እየለቃቀመች በማንሳት ተራ በተራ አራግፋ እየለበሰች ‹‹አልገባህም …ልታስቆመኝ ይገባ ነበር ፡፡እኔ የማረባ ሰው ነኝ…ደደብ ነኝ››አለች ከለቅሶዋ ሳትወጣ፡፡
‹‹አልገባኝም…እንዴ ምን ነካሽ? ወንድ እኮ ነኝ፡፡ ይሄንን የመሰለ አማለይ ዕርቃን ገላ እያየው እንዴት አልፈልግም ልልሽ እችላለው? ደግሞስ እንደዛ ብዬሽ ቢሆን ኖሮ ላንቺስ ሞራል ጥሩ ነበር እንዴ?››
ለቅሶዋን ቀጠለች….
‹‹ መቼስ አልጐዳውሽም.. እንደውም እኔ ነኝ የተጐዳውት… ጀርባዬን እንዳለ በጥፍርሽ ተልትለሺኛል እኮ!!!››
‹‹ይቅርታ ››አለቺው በስተመጨረሻ ጫማዋን እየተጫማች
‹‹አይ ይቅርታ እንድተጠይቂኝ እኮ አይደለም..ባደረግነው ነገር ሁሉ ደስተኛ ነኝ..ያንቺ ለቅሶ ነው የረበሸኝ››
‹‹ባክህ የማረባ በሽተኛ ነገር ነኝ፡፡ አሁን ተነስ ፈጠን በልና እንሂድ..››
‹‹የት ነው የምንሄደው?››
‹‹ሆስፒታል››
‹‹ብቻ እንመርመር እንዳትይኝና እንዳታስቂኝ፡፡››
‹‹ምንድነው የምንመረመረው…የመሀሪ እናት በድንገት ሽባ ሆና ሆስፒታል ገብታለች እሱን ልነግርህ ነበር አመጣጤ ፡፡ትመጣ እንደሆነ ተከተለኝ›› ብላው እየተመናቀረች ቀድማ ቢሮውን ለቃ ወጣች፡፡
ኰማንደሩም በታላቃ መደነቅ እና የልጅቷን ጤንነት እወነትም እንዳለችው እብድ ሳትሆን አትቀርም ብሎ በመጠራጠር ቢሮውን ለቆ ተከትሏት ወጣ …ወደ ሆስፒታል ለመሄድ፡፡

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እየተረሳ ነው 👍እየተጫናቹ እስቲ የናተ Like👍 ለኛ ደሞዛችን ነው

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍91
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_አምስት
:
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...ምንትዋብ ሆስፒታል በገባችበት በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ባገኘችው የህክምና እርዳታ የተወሰነ መሻሻል አሳይታለች ፡፡በሽታዋ ከበፊቱም እንዳለባት የሚታወቀው የስኳር በሽታ አሁን ከተከሰተባት ድንገተኛ የደም ግፊት በሽታ ጋር አንድ ላይ ተዳብሎ የፈጠረባት የጤና መቃወስ ነው፡፡ይህ በሽታዋ በፍጥነት ሊያሽመደምዳት የቻለው ግን በቀለመወርቅ ክህደት ምክንያት የተፈጠረባት ብስጭት ቤንዚል ሆኖ ስላቀጣጠለባት ነው፡፡
አሁን ግን ሙሉ በሙሉ ፓራራይዝድ ሆኖ የነበረው አካሏ አሁን ወደ ግማሽ ጐን ተቀይሯል፡፡ ግራ እጆን እና ግራ እግሯን በመጠኑም ቢሆን ማንቀሳቀስ ችላለች፡፡በተደረገላት ጠንካራ ህክምና ሌላም ለውጥ ታይቶባታል፡፡ተቆልፎ የነበረው አንደበቷ ተላቋል፡፡ይሄ ማለት ግን እንደ ድሮዋ ቃላትን ሰካክታ አረፍተ ነገር መስርታ ለደቂቃዎች በማንበልበል ሀሳቧን ሙሉ በሙሉ መግለጽ ትችላለች ማለት አይደለም፤ግን የቤተሰቦቹን ቋንቋ ለመለማለድ እንደሚጥር የሁለት አመት ህጻን የተሰባበሩና የተወለካከፉ ቃላቶችን ከአንደበቷ ማሾለክ ችላለች፡፡ይሄ ደግሞ ለእሷም ለልጆም ትልቅ ተስፋ ነው፡፡አይ ለእሷ እንኳን ምንም ተስፋ አይደለም ..ከተስፋ ጋር ተፋታለች… አሁን የምትፈልገው ትንሽ አቅም ማግኘት ብቻ ነው፡፡ እራሷን በመጠኑ ማንቀሳቀስ የሚያስችላት ብጣቂ አቅም..ከዛ ያቺን ያገኘቻትን አቅም እራሷን ለማጥፋት ትጠቀምበታለች፡፡አዎ ፍጹም በዚህ አይነት ሁኔታ ላይ ሆና በህይወት ለመቆየት አትፈቅድም፡፡አዎ ልጇን ደጋግማ አትበድለውም…የድህነት ማጥ ውስጥ ከታው በተጨማሪ የእሱ ሸክም በመሆን ህይወቱን ጨለማ ልታደርግበት ፈፅሞ አትፈልግም፡፡ ..ይሄ በፍፁም አይሆንም ፡፡አሁን ፈጣሪዋን የምትለምነው አንድ ነገር ብቻ ነው ..እራሷን ለማጥፋት እንድትችል የሚረዳትን ትንሽ አቅም..በቃ ጥቂት የመንቀሳቀስም ባይሆን የመንፎቀቅ አቅም ማግኘት፡፡ከዛ ያሰበችውን ታደርገዋለች፡፡
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
መሀሪ ከሳምንታት የሆስፒታል ተከታተይ ቆይታ ቡኃላ አሁን ወደቤት እያመራ ነው፡፡ወደ ቤት መሄድ የፈለገው ለሁለት ጉዳይ ነው ፡፡አንድም የገዛ ሰውነቱን ለራሱ ስለሸተተው ሊታጠብ እና ልብሱን ሊቀይር ነው፡፡ሁለተኛው ሮዛን የሚያነጋግራት ነገር ስላለው እና ቤት ሰለቀጠራት ነው፡፡ከዛ ቡኃላ ወደ እናቱ ይመለሳል፡፡ቤቱ ደርሶ የሳሎኑን በራፍ አልፎ ወደ ውስጥ እንደገባ መስታወት በሀዘኔታ እና በፍቅር ነው የተቀበለችው
‹‹ውይ..መጣህ?››
‹‹አዎ መጣው››
‹‹እኔ እኮ ምሳ ይዤ ልመጣ ነበር››
‹‹ባክሽ ሰውነቴን ልታጠብ ፈልጌ ነው የመጣሁት››
‹‹አይ ደግ አደረግክ..ጉስቁል ብለሀል እኮ.. ይሄንን ጺምህንም ብትላጨው ጥሩ ነው..በቃ ወደ ሻወር ቤት ሂድ ፤ሳሙና እዛው አለልህ..እኔ የምትቀይረውን ልብስ መርጬ አመጣልሀለው፡፡››አለችውና እሱ ወደ ሻወር ሲያመራ እሷ ወደ እሱ መኝታ ቤት አመራች፡፡ በስርዓት አጥባ ተኩሳና አጣጥፋ ካስቀመጠቻቸው ልብሶች መካከል ፓንትም ጭምር መረጠችለት እና ይዛለት ወደ ሻወሩ አመራች፡፡ሻውር ቤቱ አልተዘጋም፡፡የያዘቻቸውን ልብሶች በራፉ አካባቢ ባለ ወንበር ላይ አስቀመጠችና ወደ ውስጥ ገባች፡፡
መሀሪ ፊቱን በተቃራኒው አቅጣጫ አዙሮ ጀርባውን ለበራፉ ሰጥቶ ተገትሮ ቆሟል… ከላይ ከቧንቧው እየተስፈነጠረ ከግንሩ ላይ በመላተም ወደ ጠቅላላ ሰውነቱ እየተንቆረቆረ በሚወርደው ውሃ ሰውነቱን እያቀዘቀዘው ነው፡፡መስታወት በአንድ ሜትር ርቀት ቆማ እርቃን ሰውነቱን በፍዘት እና በተመስጦ እያስተዋለች ነው፡፡መሀሪ ከምታውቃቸው ከአብዛኞቹ የኢትዮጵያ ፖሊሶች ይለይበታል፡፡ብዙዎቹ ፖሊስ ሳይሆን አንዳንድ የከባድ መኪና ሹፌሮችን ነው የሚመስሉት…. ከመቀመጫቸው ሰፋ፤ ከሆዳቸው ገፋ ያሉ ወጣ ገባ የሰውነት ቅርጽ ያላቸው ናቸው፡፡መሀሪ ግን የሰውነቱ ቅርጽ የአትሌቶችን አይነት ነው፡፡ቁመናው የተስተካለ ፤ጡንቻው የፈረጠመ፡፡ይህን ቅርጹን ደግሞ ከልብስ ውጭ እንዲህ እርቃኑን ሆኖ ለዛውም እንዲህ እንደመስታወት በፍቅር አይን ከተመለከቱት የሚያደነዝዝ መሆኑ ብዙም አያስገርምም፡፡
ከተገተረችበት እንደመባን አለችና ተንቀሳቀሰች፡፡ከሳሙና ማስቀመጫው ሳሙናውን አነሳችና ከኃላ ተጠጋችው …ሳሙና የያዘ እጆን ጀርባው ላይ አሳርፋ አካባቢውን ማዳረስ ጀመረች፡፡መሀሪ በመመሰጥ ውስጥ ካለበት ስሜት ወጣና ፊቱን አዙሮ በትኩረት ተመለከታ…ገረመው፤ሊቃወማት አልፈለገም…ዝም አላት፤ከእሷ ጋር አታካራ ለመግጠም በዚህ ሰዓት ወኔ የለውም፡፡ የአምስት አመት ህጻን ልጆን ሰውነት እንደምታጥብ እንስፍስፍ እናት ከፀጉሩ አንስታ እስከ እግር ጥፍሮቹ ድረስ እሽት አድርጋ አጠበችው፡፡እሱ እንዳደረገችው ነው የሆነላት… ሰውነቱንም መንፈሱም በመጠኑም ቢሆን ነቃ አለለት፡፡
መስታወትም ይሄንን ዕድል በማግኘቷ እያንዳንዱን የሰውነት ክፍሉን መዳሰስ ስለቻለች እሱን ማገዝ..እሱን መንከባከብ ስለቻለች …ከእሱ ጋር ፍቅር የመስራን ያህል ስሜት ሰጥቶታል፡፡ግን ከዚህ አልፋ ድንበሩን ለማለፍ አልሞከረችም፤ለዛሬ ይሄ ይበቃታል ..ነገ ተነገ ወዲያ ደግሞ ሌሎች ከእሱ ጋር የሚያቆራኟትን አጋጣሚዎች ሊፈጠሩላት ይችላሉ..ደግሞም ይፈጠራሉ እርግጠኛ ነች፡፡ስለዚህ ‹የጅብ ችኩል ቀንድ ይነክሳል ›ተብሎ እንዲተረትባት አልፈለገችም፡፡
‹‹በቃ ተለቃለቅ እና ልብስህን ለብሰህ ና… እስከዛ ምሳ ላቀራርብልህ››አለችው በደስታ እንደተዋጠች፡፡
‹‹ምሳውን ትንሽ አዘግይው››
‹‹ምነው..ለምን?››
‹‹ሮዝ እየመጣች ነው..ትንሽ ልጠብቃት እና ከእሷ ጋር እበላለው››
ብሩህ የነበረው የመስታወት ፊት በአንዴ ሲጨልም..ፈክቶ የነበረው የውስጥ ደስታዋ በአንዴ ሲከስም ለራሷም ታወቃት.. ቢሆንም ግን በዚህ መሰበር ላይ እያለ ልትከራከረው አልፈለገችም‹‹እሺ እንዳልክ››ብላው ሻወር ቤቱን ለቃ ወደ ክፍሏ ገባች፡፡በውሀ የራሰ ልብሷን ቀየረችና ያንን ጨምቃ ውጭ በመውሰድ ካሰጣች ቡሃላ ወደ ማድ ቤቷ ገባች፡፡
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ሮዝ ጭንቅ ውስጥ ገብታለች፡፡ያስጨነቃት የኩማንደሩ መሀሪን ጥያቄ መመለስ አለመቻሎ ነው፡፡አሁን እቤቱ ድረስ እፍልግሻለው ብሎ የጠራት ለምን እንደሆነ ጠርጥራለች ..ያው የፈረደበትን የጋብቻ ጥያቄ ሊጠይቃት እንደሆነ ለእርግጠኝነት የቀረበ ጥርጣሬ በውስጦ እየተጉላላ ነው፡፡እሷ ጋብቻ አትፈልግም፡፡ፍፅሞ የትዳር ሴት እንዳልሆነች ታምናለች፡፡ዋና ችግሯ በአንድ ሰው መወሰን ነው..እንደዛ ማድረግ ለእሷ የማይታሰብ ነው፡፡..አገባች ማለት ደግሞ ታሰረች ማለት ነው…በዛ ላይ በእሷ እና በእሱ መካከል የተቀበሩ ብዙ ሚስጥሮች አሉ …ከነዚህም ውስጥ ዋና የልጅ እናት መሆኗ ነው ..ይሄንን እንዴት እንደምትወጣው ጨንቆታል…ያላት ምርጫ ሀገር ጥሎ መሰደድ ነው፡፡..እርግጥ መሀሪ የእሷን ልጅ በአካል ያቃታል …ግን የሚያቃት እህቷ እንደሆነች እንጂ ልጆ እንደሆነች አይደለም፡፡ለእሱ ሮዛ ድንግል ነች ሮዝ ሄለን የተባችውን የ10 ዓመት ልጆን የወለደችው አዲስ አበባ አጐቷ ጋር ሆና በምትማርበት ጊዜ ነው፡፡ገና 15 ዓመት ሳይሞላት፤የሃይስኩል ትምርቷን እንኳን ሳትጨርስ ነው ያረገዘችው፡፡ያረገዘችው ካፈቀረችው ሰው አይደለም፡፡አስገድዷ ከደፈራት ሰው ነው፡፡አስጠሊታው ነገር በጮርቃነቷ ማርገዞ አይደለም…አስቀያሚው ነገር ከደፈራት ሰውም ማርገዞ አይደለም፡፡አስቃያሚው ነገር ሰውዬው አጐቷ መሆኑ ነው፡፡አስቀያሚው ነገር በወላጅ እናቷ እሰከመመለክ የሚወደደው የገዛ አጐቷዋ የእናቷ ወንድም ከወንድምም አልፎ መንታ ወንድም መሆኑ ነው፡፡

ገና በዘጠኝ አመቷ ነበር እናትዬውን አባብሎ
3👍2
…የተሸለ ኑሮ ትኑር ብሎ….የተሻለ ትምህርት ትማር ብሎ ከዲላ ወደ አደዲስ አበባ የወሰዳት፡፡እርግጥ እንደለው ነበር ያደረገው፡፡ሀብት ስለነበረው ቅምጥል ህይወት ውስጥ ነበር የከተታት፡፡ በወር አንድ ሺ ብር እየተከፈለ የሚማሩበት የግል ትምህርት ቤት አስገባት፡፡አፈር አይንካሽ፤ ዓይን አይይሽ አላት፡፡እሷ አመነችው…አጐቷን ከእናቷ እኩል ወደደችው፡፡ ሰውነቷም ካለጊዜው ፋፋ…ካለወቅቱ መጐምራት ጀመረ..ጐረምሶች በእሷ መደመምና ዙሪያዋን መሽከርከር ጀመሩ..እሷም እያጐጠጐጡ የነበሩ ጡቷቾን ያስደምሟት፤ብልቷ አካባቢ እየበቀለ ያለው ፀጉሯ እያስፈነጠዛት ባለበት ወቅት አጐቷ ልጅነቷን ጨፈለቀባት፤ወጣትነቷን አጠቆረባት..፡፡ድንግል ነኝ ብላ ሳትጨርስ ሴት ሁኚ አላት፡፡ከዛም አልፎ ፀነሰች ፡፡
ትምህርቷን አቋርጣ …በሆዷ ጽንሷን ተሸክማ …በእፍረት አንገቷን ደፍታ …ሚስጥሯን በውስጧ ቀብራ…ከአዲስ አባባ ወደ ዲላ ተመለሰች፡፡እናቷ መቼም እናት ነችና ተቀበለቻት፡፡ሸሽጋት እንድትወልድ አደረገች፡፡የተወለደችው ልጅም ሄለን ተባለች፡፡ሄለን ግርማይ፡፡ግርማይ ማለት የሮዝ አባት ናቸው፡፡በዚህም የተነሳ ሚስጥሩን ከሚያውቁ በጣም ጥቂት ሰዎች በስተቀር ሮዝ እና ሄለን እናት እና ልጅ ሳይሆን እህትአማቾች እንደሆኑ ነው የሚታሰበው፡፡የሄለን አባት ማንነት ከራሷ ከሮዝ እና ከአጐቷ በስተቀር እስከዘሬ ድረስ የሚያውቅ ሰው የለም፡፡
ከዛ ቡኃላ ሌላ ሮዝ ተፈጠረች፡፡የዛሬዋ ሮዝ….ለሰው ግድ የሌላት…ለፍቅር ግድ የሌላት ሮዝ፡፡ላዬ በውበት የሚያብረቀርቅ አማላይ… ውስጧ ስብርብር ያለ ጨለማ ….፡፡የመንታ ማንነት ባለቤት ሆነች፡፡ውስጧ ካለው ብርሀን ይልቅ ጨለማው ይሰፋል፡፡ለልጇ እና ለእናቷ ካላት ፍቅር ይልቅ አጐቷ ላይ ያሳደረችው ጥላቻ በብዙ እጥፍ ይበልጣል፡፡
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
አሁን መሀሪ ጋር እየሄደች ነው፡፡ምን እንደምትለው አልተዘጋጀችበትም፡፡ገና ግራ እንደተጋባች ነው ፡፡‹‹እኔ አግብቼ ልቀመጥ ለዛውም በተክሊል .? ›› ስታስበው እራሱ አንገሸገሻት፡፡
‹‹ ግን ድንግል ነኝ ስለው እንዴት አመነኝ..?አሁን እኔ ምኔ ድንግል ይመስላል?››እራሷን ጠየቀች …መልስ ባታገኝም፡፡የኩማንደር መሀሪ ቤት ደርሳ ወደ ውስጥ ለመግባት የግቢውን በራፍ ልታንኳኳ ስትል ስልኳ ጠራ ..አወጣችና አነሳችው፡፡ኩማንደር ደረሰ ነው የደወለላት
‹‹ሄሎ ኩማንደር››
‹‹ሄሎ ልዕልት››
‹‹ልዕልት አልከኝ ደግሞ?››
‹‹ሲያንስሽ ነው..››
‹‹እሺ አመሰግናለው…››
‹‹የት ነሽ?››
‹‹ጓደኛህ እፈልግሻለው ብሎኝ እሱ ጋር እየሄድኩ ነው››
‹‹ትቆያለሽ እንዴ?››
‹‹ብዙም አልቀይ››
‹‹በጣም ለጥብቅ ጉዳይ ፈልጌሽ ነበር… እንደጨረሽ ትደውይልኛለሽ?››
‹‹በሚገባ››
‹‹ደህና ቆይልኝ …የእኔ ጣፋጭ››ብሎ ስልኩን ዘጋው፡፡እሷም ስለኩማደሩ እያሰላሰለች ወደውስጥ ዘልቃ ገባች፡፡መሀሪን ሳሎን ቁጭ ብሎ ሲተክዝ ነበር ያገኘችው፡፡ሲመለከታ የተቋጠረ ፊቱን ፈታ.. የተከደነ ከንፈሩን ገለጥ አድርጐ ተቀበላት፡፡
‹‹ምነው በሰላም…?የሆነ ከቦረና የተላከልኝ ዕቃ እኮ ልቀበል ልወጣ ስል ነው ሞቼ እገኛለው ስትል እሰቲ አናግሬህ ልሂድ ብዬ በዚሁ ጎራ ያልኩት››አለችው፡፡ቶሎ እንዲለቃት የፈጠረችው ዘዴ ነው …ቀልቧ ያለው ኩማንደር ደረሰ እፈልግሻለወ ያላት ጉዳይ ላይ ነው፡፡ከዚህኛው ለጊዜው ንዝንዝ እንጂ ምንም አታተርፍም፡፡
‹‹ምሳ እኮ እየጠበኩሽ ነው እንብላና እንጫወታለን››
‹‹እየነገርኩህ በጣም ቸኩላለው..››
‹‹ካልሽ እሺ .ያው ስለሰርጋችን እንድንነጋገር ነው››
‹‹እንዲ አስቸኳይ ብለህ የጠራሀኝ ለዛ ነው?››
‹‹እንዴ !!! ከዛ በላይ ምን ጠቃሚ ጉዳይ አለ?››
‹‹እንዴ ጊዜ አለን ብዬ ነዋ… የእናትህ ጉዳይ….. ››
‹‹ማለቴ..››
‹‹ግድ የለም አትጨነቅ ይገባኛል..እሳቸው እስኪደኑ አመት ሁለት አመት ቢሆንም መቆየት እችላለው ፡፡ ቅር አይለኝም.. ዋናው እሳቸው ብቻ ይዳኑ››
‹‹ባክሽ እኔ እንዲፈጥን ነው የምፈልገው..በቅርብ እንድንጋባ››
‹‹እንደዛማ አታደርገውም ..እናትህ አልጋ ይዛ እንዴት ነው ስለሰርግ የምታሰብው ?ሰውስ ምን ይለናል?››
‹‹እርግጥ መጀመሪያ እንዳቀድኩት ድል ያለ ድግስ አልደግስም …በመጠነኛ ድግስ መጋባት እንችላለን ዋናው የቤተክርስቲያኑ ዝግጅት ነው፡፡ቅድስ ጋብቻ በተቀደሰ ስፍራ ነው የሚመሰረተው፡፡ዋናው ድግሱ ሳይሆን ጋብቻችንን በህገ-እግዚያብሄር … በቅዱስ ታቦቱ ፊት ማስባረካችን ነው..ይሄ ደግሞ እናቴን ያስደስታታ እንጂ አያስከፋም..በጋራ ሆነን እንንከባከባታለን…እናስታምማታለን››
ንግግሩ መረራት..የሆነ እንጨት እንጨት አላት‹‹ላስብበት››
‹‹ምንድ ነው የምታስቢበት?››
‹‹ቤተሰቦቼን ላማክር ማለቴ ነው››
‹‹ምን ማማከር ያስፈልጋል? የሚቀጥለው እሁድ እኮ ሽማግሌ ልልክ ነው››
‹‹የት ነው የምትልከው?››
‹‹እናትሽ ጋር ነዋ››
‹‹በቃ አሁን ልሂደ …ሰዎቹ ዕቃውን ይዘውብኝ ይመለሳሉ… ነገ መጥቼ እናወራበታለን›› ብላ ከመቀመጫዋ ተነሳች፡፡እሱም ተከተላትና በር ድረስ ሸኛት፡፡

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
2👍2
#የተስፋይቱ_ምድር_ልጆች_ነን


በእጦት ስንኖር - አግኝተን ባናውቅም
በድህነት ሳለን...
የምድር እድሜያችን - ዘመናችን ቢያልቅም
በሰማይ ተስፋ አለን - ተስፋችን አይጠልቅም
ባለ ሀብት የሆነ...
ለእግዜር መርፌ ሽንቁር
እንደኛ ክር ሆኖ - በመንግስቱ አይፀድቅም።
እንላለን!
በተስፋ ተስፋ የማንቆርጥ...
የተስፋይቱ ልጆች ነን።
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
እርስ በርስ እየተናከስን
እርስ በርስ እየተጫረስን
አንድ ለመሆን ቢያቅተን
ላብሮነታችን ትንሳኤ - ብንታይ አንድ ላይ
ሞተን
እንድነታችን አይነጥፍም!
አንድ ነው አንድ ቢበተን።
እንላለን!
በተስፋ ተስፋ የማንቆርጥ....
የተስፋይቱ ልጆች ነን!
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ከዓለም በፊት ሰልጥነን - ከዓለም ኃላ
ብንቀርም
የተጉዋዝንበት እድሜ እንጂ - የደረስንበት
ባይኖርም
የየልባችን እግር ግን...
በመሄድ አያውቅም ዝሎ
ጥቅጥቅ ብርሐን ይገኛል...
ድቅድቅ ጨለማን ቀጥሎ።
እንላለን!
በተስፋ ተስፋ የማንቆርጥ...
የተስፋይቱ ልጆች ነን።
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ተስፋ በኛ ተስፋ ቆርጦ - ትቶን ካልሄደ
በስተቀር
ከኖርነው ጨለማ ይልቅ...
የማናውቀውን ብርሐን
በተስፋ እየሰበከች - ለምታሳየን ውብ ሀገር
የተስፋ ልጆች ነንና.....በተስፋ ተስፋ አንቆርጥም
በምንም አይነት ባህር ውስጥ ፣ አንድነታችን አይሰምጥም
በምንም አይነት መከራ
በምንም አይነት መማረር
አለት ተስፋችን አይቀልጥም።
የኖርነው ጨለማ ዘመን....
በተስፋ ከምንጠብቀው - ካልኖርነው ብርሀን
አይበልጥም!!!


ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር ከተስፋዋ ጋራ!!!

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ስድስት
:
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...ወዲያው ከመሀሪ እንደተለየች ወደ ደረሰ ጋር ነው የበረረችው፡፡የቀጠራት አንድ ዘወር ያለ ሆቴል ውስጥ ነው፡፡እንደተቀመጠች ቀዝቃዛ ቢራ ነበር ያዘዘችው….እንደመጣላት በአንድ ትንፋሽ አጋመሰችው፡፡
‹‹እንዴ ከሰሀራ በረሀ ነው እንዴ የመጣሽው?››
‹‹ያው በለው››
‹‹እንዴት?››
‹‹የጓደኛህም ንዝዝን ከሰሀራ በረሀ በላይ ልብን ያደርቃ››
‹‹ የእኔ ጓደኛማ እንደዛ አትይውም››
‹‹ባክህ እለዋለው አሁንስ በጣም ምርር እያለኝ ነው ፡፡ለእሱ ስል ሀገሩን ጥዬ ልጠፋ ነው››
‹‹አታደርጊውም…ለመሆኑ ምን አደረገኝ እያልሺኝ ነው?››
‹‹በቅርቡ ካልተጋባን እኮ ነው የሚለው››
‹‹በቅርብ…እናቱ ሳትድን?››አለ በመገረም
‹‹አዎ አይገርምም››
‹‹ትንሽ ይገርማል ..አንቺ ግን መደሰት ነው ያለብሽ…ወንዱ ሁሉ ፀረ ጋብቻ በሆነበት ዘመን ሴቶቻችን የባል ያለህ ብለው በሚቀላውጡበት ዘመን አንቺ ላግባሽ አለኝ ብለሽ ስትበሳጪ ሰውም እግዜሩም እዳይሰሙሽ››
‹‹ይስሙኛ ማግባት አልፈለግም አልኩ ….አልፈልግም፡፡››
‹‹ቆይ እሱን ነው ማግባት የማትፈልጊው ጭሩሹኑ ነው ማግባት ማትፈልጊው››
‹‹ጭራሽኑ ማግባት አልፈልግም››
‹‹እስከመቼ?››
‹‹ከበሽታዬ እስከምፈወስ ድረስ››
እነደ መደንገጥ ብሎ‹‹ከየትኛው በሽታሽ .?››
‹‹ከምታውቀው በሽታዬ››
‹‹አልገባኝም .? ››
‹‹እኔ የወሲብ በሽተኛ ነኝ…በቀደም ከአንተ ጋር የተከሰተው ለእኔ የመጀመሪያዬ ሳይሆነ በየአጋጣሚው የሚከሰት ነው፡፡በዚህ ፀባዬ ደግሞ ጋብቻ ውስጥ ገብቼ እራሴን አለሳቃይም..ለዛውም ፖሊስ አንድ ቀን እጅ ከፍንጅ ይዞኝ መንግስት ባስታጠቀው ሽጉጥ ቢደፋኝስ .?››
ኩማንደር ደረሰ ግራ ገባው…ይሄንን ውሳኔዋን ጓደኛው መሀሪ ሲሰማ ምን እንደሚሰማው ከአሁኑ ሲያስበው አስፈራው፡፡ እሱ ከአንጀቱ እንደሚያፈቅራት …በእሷ ላይ ሙሉ እምነት እንዳለው …ሊያገባት ከእሷ ወልዶ ቀሪ ህይወቱን በደስታ እንደሚያሳልፍ የፀና እምነት እንዳለው ብዙ …በጣም ብዙ ጊዜ አውርቶታል..የእሷ ሀሳብ ግን ይሄው በተቃራኒው ነው….፡፡
የጀመረችውን ጨርሳ ሌላ ቢራ ካዘዘች ቡኃላ‹‹እሺ ለምንድን ነበር የፈለከኝ?››ስትል ድንገት የጫወታውን ርዕስ በመቀየር ጠየቀችው
‹‹አንድ ነገር ላጫውትሽ ፈልጌ ነበር››
‹‹አንተም ላግባሽ እንዳትለኝ እንጂ ሌላው ችግር የለውም››
‹‹ቢሆንማ ደስ ይለኝ ነበር..ግን የባልሽ ጓደኛና ሚዜ ሆኜ ተቸገርኩ እንጂ››
‹‹እንኳንም እንደዛ ሆነ እና ቀረውብህ››
‹‹እሺ እንዳልሽው ይሁን ለጊዜው የፈለግኩሽ ለሌላ ጉዳይ ነው፡፡››
‹‹ንገረኛ››አለችው ለምንም ነገር ደንታ እንደሌላት በሚያሳብቅ ስሜት
‹‹አንድ ነገር አብረን አንድንሰራ ፈልጌ ነበር››
‹‹እኔ እና አንተ..?እንዴት ሆኖ .? ሌባና ፖሊስ ነን እኮ››
‹‹አላወቅኩም… ሌባ ነሽ እንዴ?››
‹‹ያው ነው… ኮንትሮባንድ ነጋዴንና ሌባ ምን ለያቸው…በፖሊስ ዓይን ሁለቱም ያው ናቸው››
‹‹ግድ የለም ለጊዜው በፖሊስነቴ ሳይሆን ጓደኛሽ ስለሆንኩ ነው አብረን እንስራ የምልሽ››
‹‹ስራው ምንድነው?››
‹‹ስራው አንድ ሚሊዬን ብር የሚያስገኝ ነው፡፡ከተሳካ 500 ሺ ብር ታገኚያለሽ ማለት ነው››
ከጨፈገገ እና ከሚደብት ስሜቷ ውስጥ በአንዴ ተስፈንጥራ ዋጣችና ቀጣዩን ለመስማት ተንሰፈሰፈች፡፡
‹‹እውነቴን ነው››
‹‹ለዚህ ብር አንድ ሁለት ሚገደል ሰውም ቢኖር አደርገዋለው››
‹‹ወሲብ ላይ ብቻ መስሎኝ ነበር..ለካ በሌላውም ጀግና ነሽ››
‹‹ተው ተው ዶሮ ፊት ፈንግል አይወራም..ወደ ሌላ ነገር እትገፋፋኝ አሁን ስላልከው ስራ ብቻ እናውራ››
‹‹ስራው የሚሰራው በአንድ ዙር ነው፡፡ ዕቃውን ከእዚህ ይዞ አዲስ አበባ መሄድ፤ ከዛ መሸጥ፤ ከዛ ብሩን ተካፍሎ መለያየት፡፡
‹‹እየቀለድክብኝ ነው አይደል…?››
‹‹እውነቴን ነው››
‹‹ምንድነው ዕቃው?››ጠየቀች በውስጧ ግን ይሄን ያህል ብር የሚያስገኝ ስራ በጣም ህገ ወጥ እና ከወንጀል ጋር የተገናኘ መሆኑን ባይነግራትም ገብቷታል፡፡ግን ግድ የላትም፡፡ አሁን ከገባችበት ዝብርቅርቅ ህይወት መሸሸ እና ማምለጥ የምትችለው በየትም ሆነ በየትም ጠቀም ያለ ብር ሲኖራት ነው፡፡ለዛ ደግሞ ጥሩ እድል ነው፡፡ስለዚህ ካርዱን መጫወት አለባት፡፡ለዛም በውስጧ ወሰነች፡፡
‹‹ዕቃው ሀሽሽ ነው፡፡ሀሽሹን ሰጥሻለው፤አዲስአበባ ታደርሺዋለሽ፡፡እዛ ገንዘብሽን ሰጥቶ የሚረከብሽ ሰው አለ፡፡ ከዛ በቃ..››
‹‹በቃ በቃ..››አለች ሀላፊነቷ አንሶባት፡፡
‹‹አዎ .. ግን ››
‹‹ግን ምን?››
‹‹ትንሽ ችግር አለ፡፡ ነገሩን ግልጽ ላድርግልሽ፡ሀሺሹን ከሳምንት በፊት ከአንድ አዘዋዋሪ ላይ እጅ ከፍንጅ ይዤበት ወደፖሊስ ጣቢያ እየወሰድኩት ሳለ አንድ ኩርባ ላይ ሲደርስ ሮጧ ሰው ግቢ ውስጥ ገባብኝና አመለጠኝ፡፡ ከዛ ግራ ገብቶኝ ሀሺሹን ወደቢሮ ወሰድኩና የግል ካዝናዬ ውስጥ አስቀመጥኩት፡፡እንዳላስራክበው ሰውዬውን አምጣ እባላለው ግራ ገባኝ …ቡኋላ ሳስበው ለምን ሸጬ አልጠቀምበትም የሚል ሀሳብ መጣልኝና ወሰንኩ…››
‹‹‹በጣም አሪፍ ውሳኔ ወስነሀል››አለችው
‹‹ግን አሁን…››
‹‹ምንድነው ግን ግን አበዛህ››
‹‹ባክሽ ሀሽሹን ያስቀመጥኩበት ካዝና ቁልፍ ጠፋብኝ››
‹‹ታዲያ አትገነጥለውም››
‹‹አይ እንደዛ ማድረግ አልችልም››
‹‹ለምን?››
‹‹የመስሪያ ቤቱ ህግ ነዋ..እንደጠፋብኝ አመልክቼ ከሌሎች ፖሊሶች ጋር ሆኜ ነው መገንጠል የምችለው..ያ ሆነ ማለት ደግሞ ሀሺሹ እኔ እጅ እንዳለ ታወቀ መለት ነው፡፡ ከዛ ገቢ ሆኖ ይቃጠላል፡፡›
‹‹ውይ ኸረ እኔ ልቃጠል….ምን ነካችሁ… አንድ ሚሊዬን ብር ማቃጠል ሀጥያት አይሆኑባችሁም..እግዜሩስ ይወደዋል?››ተንዘረዘረች
‹‹እንደዛ እንዲሆን ካልፈለግሽ ያለው አንድ ዘዴ ብቻ ነው››
‹‹ምንድነው ንገረኝ?››
‹‹ተመሳሳዩ ቁልፍ ባልሽ እጅ ላይ አለ … ያው እሱ ደግሞ በእናቱ ህመም ምክንያት የዓመት ፍቃድ ላይ ነው..ቁልፉን ከእሱ እጅ ሳያውቅ ማግኘት የምትችይው አንቺ ብቻ ነሽ››
‹‹በቃ››
‹‹በቃ ምነው .?››
‹‹ቁልፉን እሱ ሳያውቅ ማምጣት ከቻልኩ ሌላ እንቅፋት የለም ማለት ነው?››
‹‹ምንም እንቅፋት የለ..ቁልፉን ባመጣሽ ከ30 ደቂቃ ቡኃላ ዕቃው በእጅሽ ይገባል››
‹‹በቃ ተነስ እንሂድ››
‹‹ወዴት? ››
‹‹ቂጤ ደነዘዘ ይሄንን አስደሳች ዕቅዳቸንን እናክብረው፡፡ ደስ ሲለኝ ደስታዬን ሙሉ የሚያደርገው ወሲብ ነው..ይመችሀል››አለችው፡፡
‹‹እንዴ አግኝቼ ነው…አለና ቀሪውን መጠጥ በአንድ ትንፋሽ ጨልጥ አደረገ እና እጆን እየጐተተ ወደ ሪሰፕሽን ይዞት ሄደ …አሪፍ ክላስ ያዙና አሪፍ ለሊት ለማሳለፍ ገቡ።

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍81
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ሰባት
:
ደራሲ:-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...ኩማንደር መሀሪ በዛሬው ቀን ደስ ብሎታል፡፡ደስታው የተያያዘው ከእናቱ ጋር አይደለም.. እርግጥ እናቱም ጥሩ የጤና መሻሻል አሳይታለች ግን ደግሞ ሳትድን እቤቷ ሆና ህክምናዋን ብትከታተል ይሻላታል ተብሎ በሀኪሞቹ ስለታመነበት ወደቤቷ ከተመለሰች 48 ሰዓት አልፎታል፡፡
የእሱ የደስታ ምንጭ ሌላ ነው፡፡ደስታው የተጐተተው ከትናንትናው ውሎው ውስጥ ነው፡፡አዎ ትናንትና የልቡ ንግስት የሆነችው ሮዝ ከቀኑ አስር ሰዓት አካባቢ እቤቱ ድረስ ሳይጠራት… ሳይቀጥራት በራሷ ጊዜ መጥታ ነበር የምስራች ልትነግረው የጨለመ ልቡን በብርሀን ልታጥለቀልቅው
እንደመጣች ወደ እሱ መኝታ ቤት ተያይዘው ገብተው በራፉን ከውስጥ ቀርቅረው..ጐን ለጐን አልጋ ላይ ተጋድመው ስለነጋቸው ሲያወሩ…ስለጐጆቸው ግንባታ ሲማከሩ…ስለሰርጋቸው ዝግጅት ሲጨቃጨቁ…ስለሚጠሯቸው ወዳጆቻቸው ሲከራከሩ በየመሀሉ ሲተቃቀፉ….አልፎ አልፎም ሲሳሳሙ እስከ 12 ሰዓት ድረስ አብረው ቆዩ፡፡አዎ ሮዝ እሱ በፈለገው ቀን መጋባት እንደሚችሉ ተስማምታለታለች፤በሚቀጥለው ሳምንት ወደ ቤተሰቦቾ ሽማግሌ እንዲልክም ፈቅዳለታለች..ታዲያ ይሄ ያለስደሰተው ምን ያስደስተዋል?ይሄ ያላስፈነጠዘው ምን ያስፈነጥዘዋል?፡፡
ትናንት ጨለምለም ሲል ተለይታው ወደ ቤቷ ብትሄድም እንደከዚህ ቀደሙ ቅር አልተሰኘም ነበር …ምክንያቱም በደስታ አጥለቅልቃው ነበር የሄደችው..ደስታው ደግሞ ለሊቱን ሙሉ አብሮት ዘልቆ አሁን ድረስ አለቀቀውም፡፡በጥዋት ነው ወደ ቢሮው የገባው፡፡ከአስር ቀን ቡኃላ ዛሬ ወደ ቢሮ መመለሱ ነው፡፡ለሰርጉ ዝግጅትም ሆነ እናቱን ለከፍተኛ ህክምና ወደ አዲስአበባ ለመውሰድ ተጨማሪ የረጅም ጊዜ ፍቃድ ማግኘት ያስፈልገዋል፡፡ለዛ ደግሞ ቢያንስ ለአንድ ሳምንት ወደ ስራው ተመልሶ በእጁ ላይ ያሉትን እልባት ሚያስፈልጋቸውን ስራዎችን ማገባደድ አለበት፡፡ለዛ ነው ዛሬ ስራ የገባው፡፡
እንደገባ የወንጀል ምርመራ ዶሲዎች ላይ ነው የተጣደው..በተነቃቃ መንፈስ ላይ ስላላ ስራዎች ፈጠን ፈጠን እያሉ እየሄዱ ነው፡፡ከጥዋቱ አራት ሰዓት ቢሆንም ድካም አልተሰማውም፡፡ትኩስ ነገርም አላሰኘውም፡፡ድንገት ግን የቢሮው በራፍ ማንኰኰት ከምስጠቱ አናጠበው፡፡
ኩማንደር ደረሰ ነበር‹‹እንኳን ለቢሮህ አበቃህ››
‹‹አሜን አሜን ግባ ››አለው፡፡
ገብቶ ከፊት ለፊቱ ቁጭ አለ፡፡‹‹ደስ ያለህ ትመስላለህ?››
‹‹አዎ ባክህ ደስ ብሎኛል››መለሰለት ፈገግታውን ሳይሸፍን….
‹‹ምን ተገኘ?››
‹‹ላገባ ነው ….ሚዜ ተብዬው ተዘጋጅ..አንድ ወር ብቻ ነው ያለህ››
‹‹አትለኝም ..!!!በቅርብ ጦርነት አለ እንዴ? ችኰላው ምንድነው?››
‹‹ትቀልዳለህ …!!ነገ ቢሆን እንኳን ደስ ይለኛል››
‹‹በል ይሁንልህ..ሰራ ገብተሀል ሲሉኝ ሰላም ልልህ ነው የመጣውት፡፡ ትንሽ ስራ አለችኝ…ለምሳ አብረን እንወጣለን፡፡››አለውና ከመቀመጫው ተነሳና ወደ በራፍ ተንቀሳቀሰ
መሀሪ ‹‹ቆይ እስቲ ያንን ዕቃ ውሰድልኝ እንጂ…ምርመራው ተቋረጠ እንዴ?››
‹‹የትኛውን ነገር?››
ከመቀመጫው ተነስቶ ወደ ካዝናው እያመራ ‹‹ሀሺሹን ነዋ››አለው፡፡
‹‹አይ አንተን ላለማስጨነቅ ብዬ ምረመራውን ዘግየት አድርጌው ነው..በል ስጠኝ እንኳንም አስታወስከኝ››
መሀሪ ብዛት ካላቸው ቁልፎች መካከል የካዝናውን መክፈቻ ቢፍግ አጣው..ግራ ተጋባ…ቁልፎቹን ቆጠራቸው ሁለት ነጠላ ቁልፎች ጐድለዋል..ደነገጠ
‹‹እንዴ ምን ነካህ?››ደረሰ ጠየቀው
‹‹ከቁልፎቼ ውስጥ የጐደለ አለ…››
‹‹የጐደለ ስትል?››
‹‹እኔ እንጃ ከመሀል ጠፍቶል››
‹‹እንዴት ሆኖ ይጠፋል..?ሌላ ቁልፍ የለህም ?››ኮስተር ብሎ ጠየቀው፡፡
በደነዘዘ ስሜት ወደ ጠረጵዛው አመራና መሳቢያውን ከፈተ.ለምን አልባቱ ብሎ ያስቀመጠው ቁልፍ ነበር አነሳና ወደ ካዝናው ተመለሰ ሞከረው ተከፈተለት….ውስጡ ባዶ ነው…. ሀሺሹ ከነ ቦርሳው የለም
‹‹ያንተ ያለህ!!›› የሚናገረው ጠፋው
‹‹ምን ሆነሀል..?ምን ተፈጠረ››በድንጋጤ በድን ሆኖ መሀል ወለል ላይ ይንጐራደድ የነበረውን መሀሪን በጥያቄ ያጣደፈው ደረሰ ነበር፡፡
‹‹ሀሺሹ የለም››
‹‹የለም ማለት?››
‹‹እኔ ምን አውቃለው የምትጠይቀኝ? ያው ቦዶ ነው››
የሆዱን በሆዱ ይዞ ትወናውን ቀጠለ ደረሰ‹‹ግራ ገብቶኝ ነዋ..ቁልፍህን የሰጠኃው ሰው ነበር?››
‹‹ለማንም አልሰጠውም..እኔው ጋር ነበር››በድካም ሰውነቱ ዛለበት እና ለባለጉዳይ የተዘጋጀ ወንበር ላይ ዘፍ ብሎ ተቀመጠ..ደረሰም ተመልሶ ከፊት ለፊቱ ተቀመጠና ‹‹ታዲያ ምን ይሻላል?››አለው፡፡ በጣም የደነገጠና በነገሩ ያዘነ በሚመስል በጨፈገገ ስሜት
‹‹እኔ ምን አውቃለው …ያው ሪፖርት አድርጐ የሚሆነውን ማየት ነዋ..!!!››
‹‹እንደዛማ አናደርግም…ይሄ ደስታህ መኰላሸት የለበትም፤በቃ ባለሀሺሾቹን እስረኞች እንልቀቃቸውና ክሱን እንዝጋው››
‹‹እንደዛማ አይሆንም ››
‹‹ለምን አይሆንም?እኔም አንተም ስንጉላላ ይታይህ …አሁን ባለህበት ችግር ላይ ይሄ ሲጨመር አትቋቋመውም››
‹‹ታዲያ ምን ይደረግ? የተሸለ ዘዴ አለህ?››
ኩማደር መሀሪ አስር ለሚሆኑ ደቂቃዎች ደረሰ ባቀረበው ሀሳብ ላይ ሲያስብበት ቆየና ‹‹በቃ ምን ምርጫ አለኝ ይለቀቁ..››በማለት ተስማማ፡፡
‹‹እንዲሁማ አንለቃቸውም..በነጻ ከተለቀቁ ሀሺሹን እንደሸጥን ይጠራጠራሉ››
‹‹ታዲያ ምን እናድርግ?››
‹‹ገንዘብ ከፍለው እንዲወጡ እናደርጋለን››
‹‹ እሱን እንደፈለግክ…ግን በዚህም ብለህ በዛ ከዚህ ጣጣ ውስጥ አውጣን..››
‹‹በቃ አንተ አታስብ በእኔ ላይ ጣለው ዛሬና ነገ አስተካክለዋለው››ብሎት ተሰናብቶት ወጣ፡፡
ደረሰ ወጥቶ ከሄደ ቡኃላ ግን መሀሪ ተረጋግቶ ስራውን መቀጠል አልተቻለውም፡፡በጣም ነው አዕምሮውን የመታው.‹‹.ማን ነው በእሱ ላይ ይሄንን ሊያደርግ የሚችል…?በምን አይነት ተአምር ቁልፉ ሊሰረቅ ቻለ?››መልስ ማግኘት ስላልቻለ ቢሮውን ቆልፎ ወደ ከተማ ሄደ መጠጣት አምሮታል ፡፡ጎደኛው አሳልፎ ቢሰጠው ምን አይነት ፈተና ውስጥ ገብቶ እንደነበር ሲያስበው ዘገነነው፡፡
ሮዝ ጋር ቢደውል ስልኰ ጥሪ አይቀበልም ይላል.. በዚህ ሰዓት ቢያገኛት ደስ ይለው ነበር የትናንትናቸውን ዓይነት ወሬ ብታወራለት ደስታው ይመለስለት ነበር.ይረጋጋ ነበር.ለማኛውም ደጋግሞ ይሞክርላትና ያገኛታል..ተስፋ አድርጎ ሆቴል ገባ..ሊጠጣ፡፡
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ሆቴል እንደገባ ጠንከር ያለ መጠጥ ነው ያዘዘው …ጅን፡፡ከጥዋቱ አምስት ሰዓት ላይ ጅን…የተቃጠለ ልቡን ይበልጥ እንዲያኮማትርለት ነው፡፡አንደኛውን ደብል ጨርሶ ሁለተኛውን እንዳዘዘ ሌላ አስተናጋጅ ወደ እሱ ቀረበ በአይን ይተዋወቃሉ፡፡እዚህ ቤት ብቻውንም ሆነ ከጓደኛቹ ጋር ሊስተናገድ ሲመጣ ብዙ ጊዜ አስተናግዶታል
‹‹ሰላም ኖት ኩማንደር? ››
‹‹ሰላም ነኝ ››
‹‹ጐደኛዎት አብሮት አልመጣም እንዴ? ››
‹‹የትኛው? ››አለው ኮስተር ብሎ
‹‹ኩማንደር ደረሰ>>.
‹‹አልመጣም..ምነው? ››
‹‹አይ ፈልጌያቸው ነበር››
‹‹እኮ ለምን? ››
‹‹አይ ዛሬ እኛ ሆቴል ነበር ያደሩት..የእሷቸው ይሁን የፍቅረኛቸው አላውቅም ቁልፍ ጥለው ሄደዋል..እሱን ልሰጣቸው ነበር››
‹‹ፍቅረኛቸው ስትል? ››
‹‹ያው ፍቅረኛው ማለቴ ነው.ማታ አብራው እዚህ ያደረችው››
መሀሪ ግራ ተጋባ እስከሚያውቀው ድረስ በዚህን ወቅት ደረሰ ፍቅረኛ የለውም‹‹ይሁን ቁልፉን አምጣው እኔ ሰጥልሀለው››አለው

ልጁ በእጁ ይዞ የነበረውን ሁለት ነጠላ ቁልፍ እጁ ላይ አስቀመጠለት..መሀሪ ነዘረው.በትኩረት አየው..አገላብጦ መረመረው..አዎ የገዛ ራሱ ቁልፍ ነው።
👍31
ሁኔታውን በንቃት ይከታተል የነበረው አስተናጋጅም ግራ ተጋባ
‹‹አብራው የነበረችው ምን አይነት ልጅ ነች ? እስኪ ንገረኝ? ››
‹‹የልጅቷን ሁኔታ… አካላዊ ቅርጾን ቁልጭ ባለ አገላለፅ ምሰል ከሳች በሆነ ትረካ አስቀመጠለት…
መሀሪ ነገሮች በእሱ ላይ ሲመሳጠሩ የነበሩ ጉዳዩች በየደርዛቸው ፍንትው ብው እየተገለጹለት ነው ፤ልቡ በንዴት እየተኰማተረች እንደሆነ ለራሱ ተሰማው
‹‹ስሟን ሲጠራት አልሰማህም?››
ልጁ ግራ ተጋባ ‹‹ምነው በቀረብኝ..ምስጋና እና ጉርሻ ፈልጌ ብመጣ ምርመራ ይጠብቀኝ..ድሮም የፓሊስ ነገር መላቅጥ የለውም ››አለ በውስጡ
‹‹ሰምቼ ነበር ግን ጠፋኝ››
‹‹እስቲ ለማስታወስ ሞክር››
‹‹የሆነ የቀለም ስም መሰለኝ››
‹‹ጽጌረዳ››
‹‹አይደለም››
‹‹ሮዝ››
‹‹አዎ ትክክል.. ሮዝ ብሎ ሲጣራት ከአንዴም ሁለቴ ሰምቼዋለው››አረጋገጠለት፡፡
መሀሪ አፈረ..በጣም አፈረ …..ያፈረው በራሱ ነው..እንዴት በጣም የሚያፈቅራት ፍቅረኛው እና በጣም የሚወደው ጓደኛው አይኑ ስር እንዲህ ያጃጅሉታል‹‹…ምን ያህል ነገሮች የማይገቡኝ ደደብ ሰው ነኝ…ከአንድ የፖሊስ ሞኮንን ይህ ይጠበቃል ቀሺም ነኝ›› አለ በውስጡ..እራሱን ረገመ..እራሱን ወቀሰ‹‹ተገትሮ የሆነ ነገር እንዲለው ወደሚጠብቀው አስተናጋጅ ቀልቡን መለሰና‹‹ይሄውልህ ይሄ ቁልፍ የእኔ ነው …ተውሶኝ ጥሎብኝ ነው..በዚህም ምክንያት እኔ ጥለህብኛል ስለው እሱ መልሼልሀለው ብሎ ስለተጨቃጨቅን ተጣልተን ነበር..አሁን አዎ ሰጥተኸኝ ነበር እኔ ነኝ የረሳውት ብዬ ይቅርታ ልጠይቀው እፈልጋለው… ጓደኛዬ እንዳይሳቀቅብኝ ..ስለዚህ ባክህ አንተ አትንገረው…..››
‹‹አረ ችግር የለውም ››አለ ልጁ
መሀሪም ወደ ኪሱ ገባና የተወሰኑ ዝርዝር ብሮች አወጣና አስጨበጠው..ልጅ በደስታ እየፈነጠዘ ወደ ስራው ተመለሰ..ከዛም ሙሉ ጠርሙስ ጅን አዘዘ..ይበልጥ ሊጠጣ… ለራሱ ሽንፈት ፅዋ ሊያነሳ...

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍1
#ሀገር_አልባ_ባለ_ሀገሮች
:
ሁሉም የራሱን ዘር ፣ ከሌሎች ያገዝፋል
ሁሉም የብሔሩን ፣ ክብር ይለፍፋል
ሁሉም ትልቅ ነኝ ሊል ፣ ይኮለታተፋል
እንደ ሀገር የሚያስብ ፣ እንዴት አንድ ይጠፋል?
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
እንግዳ ተቀባይ
ጨዋ ህዝብ ነን ባይ
ስድብ እያመረተ
ውረፋ ብሽሽቅ ከተበራከተ
እኔነት አብቦ ፣ እኛነት ከሞተ
አፎች ፍቅርን ሰብከው ፣ ልቦች ቂም ከጫኑ
አንድነን የሚሉ ከተበታተኑ
ሰው እየዘነጉ
"ሀገሬን አልረሳም " ፣ እያሉ ቢዘፍኑ
ስላቅ ነው ትርጉሙ
ሮሮ ነው ዜማው ፣ ሾርኔ ነው ግጥሙ።
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ያለፈውን አልፈን
ጨለማውን ገፍፈን ፣ ብርሐን ሳንሰበስብ
ይነጋል እያለ
አንዱ አንዱን ሲጠልፍ ፣ አንዱ አንዱን ሲስብ
አንዱ አንዱን ሲጓትት ፣ ሆነን የአለም ጭራ
እያልን ብንዘፍን ፣ ሀገሬን አደራ
ሹፈት ነው ትርጉሙ
የቀልድ ነው ዜማው ፣ ቅዠት ነው ትርጉሙ
አደራ እየበሉ ፣ አደራን ማቀንቀን
እንዴት ብርሐን እንይ
እኛ እየታወርን ፣ ይነጋል ባልነው ቀን
ለውጥ ኬት ይመጣል
እኛ ሳንለወጥ ፣ ለውጥ ቢናፍቀን?
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
እናም እኔ አንዳንዴ
ሲከፋኝ ሲከፋኝ ፣ የማንጎራጉረው
አንድ ዘፈን አለኝ
እንባ ሆኖ የሚያልቅ ፣ በሳቅ ስጀምረው
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
እናም የኔ ዘፈን
"ሀገሬን አልረሳም
ወገኔን አልረሳም"
በምትሉት ዘፈን ፣ አትፈልጉኝ ነገር
እንዳገር ሳናስብ ፣ ኬ'ት አመጣችሁ ሀገር?!!

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ስምንት
:
ደራሲ፡-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
..መሀሪ ሕይወት ቀፋዋለች.. በሰዕታታ ልዩነት ሁሉ ነገር ጭልምልም ብሎበታል…..ሰው ሰውን ሲቀየምና ሲጠላ ምንም አይደል…ሰው አምላኩን ቢቀየምም ምንም አይደል(ምክንያቱም አምላክ ለምን ተቀየማችሁኝ ብሎ እልክ በመጋባት ጥበቃውን አያቋርጥም)…. ሰው ራሱን ከተቀየመና ከጠላ ግን አደገኛ ነው…
እራሱን የጠላ ሰው ለምንም ነገር ደንታ አይኖረውም..እራሱን የጠላ ሰው ነገሮችን በቀና ሁኔታ የማስተካከል ተነሳሽነቱ ዜሮ ነው….እራሱን የጠላና የተጠየፈ ሰው አለምን እንዳለ ለማጥፋት እና ለማውደም ዝግጁ ነው፡፡ መሀሪም በአሁኑ ጊዜ እንደዛ ነው የሆነው..እራሱን ነው የጠላው..እራሱን ነው የተጠየፈው፡፡
ግማሽ ጠርሙስ ጅን ቢጋትም የደረሰበት በደል ካሰከረው በላይ ሊያሰክረው አልቻለም፡፡ያም አበሳጭቶታል …ሂሳቡን ከፍሎ ሆቴሉን ለቆ ወጣ፤ ወደ ቤቱ አልሄደም፡፡ሽጉጡን በሽንጡ አንደሸጐጠ ቀጥታ ወደ እነ-ሮዝ ቤት ነው የሄደው፡፡
ከተማውን ለቃ እንደወጣች ያውቃል…ቢሆንም አላመነም..ተመልሳ መጥታ ሊሆን ይችላል..እቤት ቁጭ ብላ ሊያገኛት ይችላል..ካገኛት ደግሞ ሊያናግራ ይፈልጋል፤ ስለሁሉም ነገር በዝርዝር እንድታስረዳው ሊያስገድዳት ይፈልጋል፤ነግራው ስትጨርስ እዛው በተቀመጠችበት በያዘው ሽጉጥ ሊደፋት ይፍልጋል..ደፍቷት ሊገላግላት.. ከዛ የተቀሩትን ጠላቶቹን ለማሳደድ ይሄዳል ቀለም-ወርቅና ደረሰን እንደ ደረሰ ከቆርቆሮ የተሰራውን የአጥር በር ከመጠን በላይ በሆነ ኃይሉ አንኳኳ‹‹ኸረ ማነው? ቀስ.. መጣው ደርሼያለው››ከውስጥ የሚሰማው ድምጽ ነው::ቀኝ እጁን ወደ ሽጉጡ ላከና ደባበሰው፡፡በራፉ ተከፈተ ፤ ሄለን ነበረች፡፡ገፍትሯት ወደ ውስጥ አልፎት ገባ፡፡ እሷም ወደኃላዋ ዞራ ተከተለችው፡፡ግራ አጋብቷታል ፤ ከዚህ በፊት አንድ ሁለት ቀን ከሮዝ ጋር እቤት መጥቶ አይታው ስለነበረ በመጠኑ ታቀዋለች ..ግን የዛሬው ሁኔታ አላማራትም፡፡እሱ የሳሎኑን በራፍ አልፎ ገብቶ ፊት ፊት ያገኘው ወንበር ላይ ተቀመጠ፡፡ሄለን ከኃላው ደርሳለች …ስለደነገጠች ፊት ለፊቱ ተገትራ እያስተዋለችው ነው
‹‹እህትሽን ጥሪልኝ››
‹‹እኔ እህት የለኝም››አለችው
‹‹እየቀለድሽ ነው… ?ሮዝ ምትባለውን ልጅ ወይም ሴትዬ ጥሪልኝ››አላት
‹‹አሀ እሷን ነው እንዴ?››አለችና ወንበረ ስባ ከአቅራቢያው ተቀመጠች
‹‹ያናደደችህ መሰለኝ…ቢሆንም ግን የለችም›››
‹‹የት ሄደች?››
‹‹የት እንደምትሄድ እንኳን እኔ እሷ ራሷ ምታውቀው አይመሰለኝም..ሰው አድርገሀታል እንዴ…..?ጤነኛ እኮ አይደለችም››
‹‹እህትሽን አትወጂያትም እንዴ? ››
‹‹ይቅርታ እህቴ እንዳልሆነች የነገርኩህ መሰለኝ ..ነው ወይስ እሷ እህቷ ነኝ አለችህ…?››
‹‹አዎ ብላኛለች››
‹‹እንግዲያው ሸውዳሀለች››
የልጅቷ ንግግር ብዥ ያለበትን አዕምሮውን ይበልጥ ብዥ እንዲልበት እያደረገው ነው..ስለዚህ ከእሷ ጋር እየወራ መቀጠል አልፈለገም‹‹እሺ እናትሽ የሉም? እሳቸውን ጥሪልኝ ›› ምንም ቢሆን ከትልቅ ሰው ጋር ባወራ ይሻላል በሎ ስላሰበ ነበረ የጠየቀው…
‹‹የለችም …ለቅሶ ብላ አሁን ቅርብ ጊዜ ነው የወጣችው››
ምርጫ ስለሌለው ጥያቄውን ቀጠለ‹‹ቆይ ቅድም አታላሀለች ስትይ ምን ማለትሽ ነው?››
‹‹እህቴ ነች ያለችህ ውሸቷን ነው ….እህቷ አይደለውም …››
‹‹ምኗ ነሽ ታዲያ?›››
‹‹ምኖ እንደሆንኩ ወይም ምኔ አንደሆነች መናገር ያመኛል..ያስጠላኛልም››
ይህቺ ልጅ ካሰበው በላይ ጠንከር አለችበት‹‹ባክሽ ለእኔ ስትይ ሞክሪ››
‹‹ከማይታወቅ ዘር ከማይታወቀው አለም ወደዚህኛው አለም ያመጣችኝ…የቅብጠቷ ውጤት የሽርሙጥናዋ ፍሬ ነኝ››
‹‹ማለት ልጆ ነኝ እያልሽ ነው?››
‹‹አይ ልጆ ነኝ አላልኩም ..ፀንሳ አርግዛ የወለደቺኝ ግን እሷ ነች››
ተስፈንጥሮ ከተቀመጠበት ተነሳ‹‹..ደደብ ነኝ…የማልረባ ነኝ..ማንም እንደፈለገው ጢባ ጢቤ ሲጫወትብኝ የኖረ ቀሺም ሰው…›››እየለፈፈ ወደ ውጭ አመራ…. ከኃላው ተከትላው እያወራችው ነው‹‹ትጐዳሀለች…. ከእሷ ራቅ… ፍፁም ጥሩ ሰው አይደለችም…. ነግሬሀለው ድምጣማጥህን ነው የምታጠፋው››
የግቢውን በራፍ ተራምዶ ከወጣ ቡኃላ ወደኃላው ዞረና‹‹እርሺው ››አላት
‹‹ምኑን?››አለችው ደንግጣ
‹‹ምክርሽን ነዋ..››
‹‹ለምን?››
‹‹ጊዜው ያለፈበት ምክር ነዋ..ልቤን አድቅቃ በትናዋለች..ማድረግ የምትችለውን ነገር ሁሉ አድርጋኛለች..ማንነቴን ከጓደኛዬ ጋር ተባባር አውድመዋለች…
ሰባአዊነቴን አክስማው በምትኩ …የሚቧጥጥ ጥፍር ያለው..ያገጠጠ ስል ጥርሶች ባለቤት የሆነ.. የሚዘነጣጥል… የሚሸረካክት አውሬ በውስጤ ፈጥራብኛለች…. መጥፎ ሰው ነች ነው ያልሺኝ…? መጥፎማ ፈፅሞ አይግልጻትም.ፍፅም…››እየለፈለፈ መንገዱን ቀጠለ
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
አሁን መሀሪ ሻንጣውን እያዘጋጀ ነው..ወደ የት እንደሚሄድ አያውቅም..ግን ለተወሰኑ ቀናት ከዚህ አካባቢ ዞር ማለት አለበት፡፡..የተረጋጋ ቦታ ሆኖ የተረጋጋ ነገር ማሰብ ይፈልጋል፡፡ከአሁን ወዲህ በዕቅድ ነው መንቀሳቀስ ያለበት፡ሶስት ሰዎችን የመበቀል ዓላማ…ሻንጣውን ይዞ ወደ ሳሎን ወጣ ወንበር ስቦ አረፋ አለና መስታወትን ጠራት.እየተክለፈለፈች መጣች
‹‹መሀሪ ፈለከኝ?››
‹‹አዎ አንዴ ቁጭ ብትይ …ማማክርሽ ነገር ነበረ››እያጉተመተመች መጥታ ከፊት ለፊቱ ቁጭ አለች
‹‹ምነው ፊትሽን ጣልሺው?››
‹‹ያው ገብቶኛል… ሰርግ ደግሺ ልትለኝ አይደል?››
‹‹አይደለም..ሠርግ የሚባል ነገር እዚህ ቤት መቼም አይኖርም››
በደስታና ግራ በመጋባት ዘላ ተነሳች …መልሳ ተቀመጠች‹‹ማለት አልገባኝም..ትናት እኮ በቅርብ ቀን እንደምታገባ ነግረኸኝ ነበር››
‹‹ዛሬ ደግሞ መቼም እንደማላገባ ይሄው ነገርኩሽ››
‹‹አይ አሪፍ ነው››
‹‹አሪፍ ሆነም አልሆነም አሁን አንድ ውለታ እንድትውይልኝ ፍልጌ ነበር››
‹‹ማ ..እኔ››
‹‹አዎ አንቺ››
‹‹ሙቺልኝ ብትለኝ እንኳን ሞትልሀለው››
‹‹ያን ያህል እንኳን አላስቸግርሽም..ለአንድ ሰምንት የሆነ ቦታ ልሄድ ነበር …እስክመጣ እናቴን ልትንከባከቢልኝ ትችያለሽ››
‹‹አንድ ሳምንት ማለት ሰባት ቀን ነው አይደል ..?››
‹‹አዎ ሰባት ቀን ነው››
‹‹ሰባት አመትም ቢሆን በትዕግስት እንከባከብልሀለው….››
‹‹በጣም አመሰግናለው ›› በማለተ ከኪሱ ብር አወጣና ‹‹ለማንኛውም ያዢው›› ብሎ ሰጥቷት እናቱ ወደተኛችበት ክፍል አመራ …ሊሰናበታት።

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍42
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ዘጠኝ
:
ደራሲ:-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
ስትኖሪ/ሳትኖሪ
ፀሀይ ወረተኛ -ከምስራቅ ፈንጥቃ…በምዕራብ ለመጥለቅ ጨረቃም ተወልዳ ብርሀን ለመፈንጠቅ
በፍቅር እያለው…..አቤት ሲቸኩሉ
መጥተው ሳይጨርሱ ..ወዲያው ይጠፋሉ
አዎ እውነቴን ነው…………..
አቅፌሽ ሳልጨርስ…ጨለማው ይገፋል
ስሜሽ ሳላጣጥም..ሙሉ ቀን ይበናል
ቀኑ ሳምንት ሆኖ..በወር ሲጠቃለል
ወቅቶች ተፈራርቀው ..አመት ሲንከባለል
ባፈቀርኩሽ ጊዜ ….መች አስተውልና
አይኔም መላ ቀልቤም…. ካንቺው ነበርና
ዛሬ ግን ስትነክሺኝ……
ሰዓቱ አይቆጥር…ሁሉም ዝግ… ሁሉም ዝም
ከጨለመ አይነጋ…ከነጋ አይጨልም
ከሄድሽ ሳምንትሽ ነው…አውቃለው አልቆየም
ሳምንት ስንት ቀን ነው…? ሆነብኝ ዘላለም
ከምንዛሬው ነው…ልዩነት ስሌቱ
በማጣት ውስጥ ሲሆን …መከራ ርዝመቱ
እስትናፋሴ ነበር…‹ፍቅርሽ ›ትናንትና
ዛሬም ‹በቀል ›አለኝ….ህይወቴን ያፀና
፦፦፦፦፦
ይሄን ግጥም በሮዝ ከተከዳ ከሳምንት ቡኃላ በቁዘማ ውስጥ ሆኖ የፃፈው ነበር..እንሆ ሁለት አመት ሙሉ በቃሉ ሸምድዶት ዜማ ፈጥሮት የሚያዜመው የልቡ ብሄራዊ መዝሙር አድርጎታል…የድሮ እሱነቱ ከስሞና ሞቶ አዲስ አይነት ሰው ከውስጡ ተወልዶ እንዲህ ጠንክሮ ሲያድግና ሲጎለብት ይሄ ከለይ ግጥሙ የቀረበው ግጥም ዜማ ለብሶ በእሱ አንደበት ሲንቆረቆር የሚሰማውን ሰው ልብ በሀዘን ሲቦረቡር የእሱን ልብ በተቃራኒው ሲያደድር ነበር ያለፉት ሁለት አመት ያለፈት…….ሁለት ጭለማ አመታት..ሁለት ሚስጥራዊ ዓመታት…..
/
/
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ሮዝ አዲስ አበባ ከገባች ሁለት አመት ልታገባድድ ጥቂት ነው የቀራት፡፡ሁለት በጣም ፈጣን እና በድርጊት የታጨቁ ዓመታት ናቸው፡፡ከኩማንደር ደረሰ ጋር በመመሳጠር ፍቅረኟዋን መሀሪን በመክዳት ባገኘችው ገንዘብ ህይወቴን ሊያሻሽልልኝ ይችላል ብላ ያሰበቻቸውን የተለያዩ ስራዎችን ስትሰራ ቆይታለች፡፡አሁን ግን ሌላ አዲስ ስራ ለመጀመር ደፋ ቀና እያለች ነው፡፡ሳሪስ አካባቢ አስር መኝታ ክፍል ያለው ሆቴል ሰሞኑን ተከራይታለች፡፡ተከራታም ወደስራ ለመግባት እያሳደሰችው ትገኛለች፡፡የደከሙ ወንበሮችን በአዲስ ወንበር መቀየር …ዋናውን ሆቴል ሆነ መኝታ ክፍሎቹን ቀለም ማስቀባት…. ሚስተካከሉ ነገሮችን ማስተካከል ላይ ትገኛለች .. ደግሞ ይሄን ስራዋን በሀሳብም ሆነ በጉልበት የሚረዳት ሰው አግኝታለች፡፡ልጁ አቤል ይባላል አፋቃሪዋ ነው..የ6 ወር ፍቅረኛዋ ያ ማለት ግን በዚህ ሁለት አመት ውስጥ ከዲላ ለቃ ፍቅረኛዋን መሀሪን ትታ አዲስ አበባ ከገባች ቡኃላ ተረጋታ አንድ ፍቅረኛ ይዛ መኖር ጀምራለች ማለት አይደለም …ብዙ ወንዶች በህይወቷ በየቀኑ እየገቡ ሚወጡ አሉ፡፡ የአቤልን ልዩ የሚያደርገው ግን በተደጋጋሚ ጊዜ እና ላልተቋራረጠ ጊዜ ከእሷ ጋር ረዘም ላሉ ጊዜያቶችን ማሳለፍ መቻላቸው ነው፡፡
አቤልን እዚሁ አዲስ አበባ በአጋጣሚ ነው ያገኘችው፡፡አቤል ስራው ከእሷ የስራ እንቅስቃሴ ጋር የሚሄድ ሆኖ ሳይሆን እንዲሁ የአጋጣሚ ወይም የእህል ውሀ ጉዳይ ነው ያጋጠማቸው፡፡
አንድ ቅዳሜ ለሊት ጭፈራ ቤት ውስጥ ነው የተገናኙት፡፡መቼስ ሁሌ የፍቅር ቅደም ተከተሉ መተዋወቅ..መፋቀር..መሳሳም(መተሻሸት)..ከዛም ወደ አልጋ መሄድ ሊሆን አይችልም፡፡አንዳንዴ ከመጀመሪያው መተዋወቅ ቀጥሎ የመጨረሻው አልጋ ላይ መውደቅ ይከተልና ሌሎቹ ዋል አደር ብለው ይከተሉ እና ያስደንቁን ይሆናል…ይህ ክስተት በሮዝ ህይወት ውስጥ ተደጋግሞ የተከሰተ ነው ፡፡ለአቤል ግን አስገራሚና ለመጀመሪያ ጊዜ በህይወት የተከሰተ ክስተት ነበር፡፡ሚገርመው ደግሞ አቤል እንዲህ አይነት ያልተለመዱ እና ከዘወትሩ ያፈነገጡ ነገሮች ይማርኩታል… ያስገርሙታልም፣.ለዚህም ይሆናል ደራሲ የሆነው፡፡
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
አሁን ሮዝ እና አቤል አንድ ላይ ሰራተኞች ሲሰሩ የዋሉትን የሆቴሉን እድሳት ስራ እየጐበኙ ነው፡፡ዋናውን ቤትን ካዩ ቡኃላ ወደ ቤርጐዎቹ ነው ያመሩት
‹‹የመረጥነው ቀለም ግን እንዴት ነው..?ሰው የሚወደው ይመስልሀል?››
‹‹በጣም እንጂ ..እጅግ በጣም መንፈስን የሚያረጋጋና የደስታ ስሜት የሚፈጥር ነው…..በጣም ወድጄዋለው፡፡››
‹‹እሱማ እኔም ደስ ብሎኛል..ደግሞ ከመቼው ደረቀና አልጋውን አስገቡት››አለችው፡፡
‹‹እንዴ ትናንት እኮ ነው ቀብተው የጨረሱት… ዛሬ ሌሎችን ነገር ሲያስተካክሉ ነው የዋሉት››አብራራላት፡፡
እያንዳንዱን መኝታ ክፍልን ውስጡ በመግባት እየተመለከቱ ስለጐደለው ነገር እንዴት መስተካከል እንዳለበት አስተያየት እየሰጡ ወደሚቀጥለው ክፍል መጓዝ ጀመሩ፤ አንደኛውን መኝታ ክፍል ሁለተኛውን.ሶስተኛውን አራተኛውን…አምስተኛው ላይ ግን የደከማቸው ይመስል ወደ ውስጥ እንደገቡ አልጋው ላይ አረፋ አሉ፡፡…ቀድማ አረፍ ያለችው ሮዝ ነች፡፡እሱም ያለምንም ንግግር ተከትሎት ከጐኗ ተቀመጠ እና ማውራት ጀመሩ …አንድ የሚከነክነውን ነገር በመጠየቅ ጫወታውን ጀመረ
‹‹ሁል ጊዜ ጠይቅሻለው እያልኩ እየረሳውት..ለመሆኑ የየት ሀገር ልጅ ነሽ….?››
‹‹ምነው ምን አሳሰበህ…?››ስትል ጥያቄውን በሌላ ጥያቄ መለሰችለት… ጥያቄው ወቅቱን ያልጠበቀ ያለቦታው የቀረበ ስለመሰላት ተገርማለች፡፡
‹‹አይ አሳስቦኝ ሳይሆን እንዲሁ ለማወቅ ያህል ነው፡፡›.ሲል ማብራያ አከለበት፡፡እውነታው ግን አቤል ስለእሷ ህይወት ለማወቅ አሳስቦት እንኳን ባይሆነ አጐጉቶት ነው ቢባል ያስኬዳል፡፡… ይሄው ከተገናኙ ጀምሮ ስለሀገሯ ስትናገር …ስለቤተሰቦቾ ስታወራ ስምቶ አያውቅም….፡፡እንዴት ሰው አንድ ቀን እንኳን ድንገት አምልጦት ስለ ሀገሩ አያወራም? እንዴት ሰው ድንገት አምልጦት ስለ አብሮ አደግ ጓደኞቹ አያወጋም….?እንዴት እከሌ ናፈቀኝ ብሎ ስለወላጆቹ አያማርርም…?ይሄ ጉዳይ ነው ግርምትን የጫረበት …
‹‹ለማወቅ ያህል ስትል … አውቀህ ምን ይጠቅምሀል?››መልሳ ጠየቀችው
‹‹ምን ያደርግልሀል ስትይ ምን ማለትሽ ነው ?ምንም ቢሆን ፍቅረኛሽ መሆኔ ቀረ እንዴ?››አላት፡፡
ደፍራ ነህ ወይም አይደለህም ብላ ልትከራከረው አልቻለችም…ግን በሌላ መንገድ መለሰችለት‹‹እሱማ ድሮ ቀረ …ፍላጐት ቢኖርህ ኖሮ ከስድስት ወር በፊተ ገና ስንገናኝ ትጠይቀኝ ነበር›.
‹‹የዛን ጊዜማ ረሀቤ አንቺን ለማግኘት እንጂ ስለ አንቺ የህይወት ታሪክ ለማጥናት አልነበረም…አሁን ግን ወደፍቅርሽ መረብ ጠልቄ ገብቼያለው….ስለ አንቺ ማሰብና መጨነቅ ከጀመርኩ ሰነባብቼያለው››ሲል መለሰላት አቤል ፡፡
እውነትም እንዳለው ስለእሷ ህይወት ዝርዝር ያለፈ ታሪኮን ለማወቅ መጓጓት ከጀመረ ቀናቶች ተቆጥረዋል፡፡ይህ ፍላጐቱ የመነጨው ለእሷ ካለው ፍቅር የተነሳ ወይም ወደፊት ሊያገባት በመወሰኑ ምክንያት ቀድሞ ስለማንነቷ ለማጥናት ካለው ፍላጐት የተነሳ አይደለም፡፡ሮዝን ዋና ገጸ ባህሪው አድርጐ ሶስተኛ ልብ ወለዱ መጽሀፍን መጻፍ ይፈልጋል፡፡ለዚህ ያነሳሳው የእሷ ጠቅላላ ያልተለመደ ሁኔታዋ ነው፡፡የወሲብ ስሜቷን የምትገልጽበት መንገድ የተለመደና ጤነኛ አይነት አለመሆኑ ..በደቂቃዎች ውስጥ መንታ ስሜቶችን ማስተናገዶ....ፍልቅልቅ ሳቂታና ተጫዋች ሆና ያለችበትን አካባቢዋን በደስታ ሞልታው እያለ ከመቅፅበት ደግሞ የፊቷ ፀዳል ከስሞ እርብሽብሽ ባለ ስሜት ተውጣ መገኘቷ፡፡እንዲህ አይነቱ በእሷ ላይ የሚታይባት ተፈራራቂ የስሜት መዋዠቅ ነው በጣም የሳበው.እና እያዋዛ ታሪኳን ማጥናት..ማንነቷን ፈልፍሎ መገንዘብ እና ለመጽሀፉ ጭብጥ ማግኘት አቅዶ መስራት የጀመረው፡፡
‹‹የዲላ ልጅ ነኝ››አለችው..ረጅም ትንፋሽ ወሰደችና ቀጠለች‹‹…የልጅነት ጊዜዬን ግን ያሳለፍኩት እዚሁ አዲስ አበባ ነው፡፡››
‹‹አዲስ አበባ? ቤተሰቦችሽ
👍5
እዚህ ናቸው ማለት ነው?››
‹‹አይ እዛው ዲላ ናቸው.››
‹‹ታዲያ አዲስ አበባ ማን ጋር ነበረ የምትኖሪው?››
‹‹አንድ አጐት ተብዬ ሰይጣን ሰውዬ ጋር..ይቅርታ ሰይጣን ብዬ ክብር ሰጠውት..ሰይጣንነትም አይገባውም›.
‹‹አልገባኝም››
‹‹ተወው… ይሄኛው የህይወቴ ክፍል በቀላሉ አይገባህም…እጅግ ጥቅጥቅ ጨለማ ከመሆኑ የተነሳ ወደውስጥ ብትገባም ምንም ሊታይህ አይችልም››አለችው፡፡
ብዙ ሊጫናት ስላልፈለገ ወደሌላ ጥያቄ ተሸጋገረ፡፡‹‹እናትና አባትሽ ዲላ ናቸው ማለት ነው?››
‹‹አይ አባቴ የለም…. እናቴና ልጄ ናቸው እዛ ያሉት››ብላ ያልጠበቀውን እስደንጋጭ ነገር ነገረችው
‹‹ልጄ ነው ያልሽው?››
‹‹አዎ ልጄ?››
‹‹ልጅ አለሽ? ››
‹‹አዎ ከዲላ ስለቅ አስራ ሁለት…አመቷ ነበር …አሁን አስራ አራት ጨርሳ በሚቀጥለው ወር አስራ አምስተኛ አመቷን ትይዛለች...ብታያት እንዴት አይነት ቆንጆ የምታምር ልጅ አለቺኝ መሰለህ ››አለችው ፊቷ ላይ የሚያንፀባርቅ ብርሀናዊ ደስታ ፈሶባት፡፡
‹‹እየቀለድሽ ነው?››
‹‹በፍጹም››
‹‹በስንት አመትሽ ወልደሽ ነው የአስራ አራት ልጅ ማድረስ የቻልሽው?፡፡››
‹‹ገረመህ አይደል ….?በዕቃ`ቃ ጫወታ ብዬ አረገዝኩ የእውነት ወለድኩ››ብላ እውነታውን በቀልድ ሸፋፈነችበት ፡፡
‹‹,ታዲያ እየሄድሽ ትጠይቂያቸዋለሽ..?››ሌላ ጥያቄ
‹‹በፍጹም… ዲላ ከተማ ከረገጥኩ ሶስተኛ አመቴን ልይዝ ነው ››
‹‹በስልክስ?››
‹‹ለአንድ አመት ያህል አገኛቸው ነበር..አሁን ግን ስልኬን አያነሱም …..››
‹‹አልገባኝ ለምን?››
‹‹ተቀይመውኛል ..ጠልተውኛል››
‹‹እኮ ለምን?››
‹‹ የዛሬ ሁለት አመት እናቴ እዚህ መጥታ ነበር ፡፡ለምን መሰለህ?አጐቴ ታሞ ልትጠይቀው ..ይህ አጐቴ ያልኩህ የእኔ አሳዳጊ የእሷ ደግሞ መንትያ ወንድሞ ነው፡፡እና እንዳልኩህ በመጣች ጊዜ ደውላልኝ ነበር፡፡ እኔ ግን በህይወቴ በጣም ወደምጠላው ሰው ቤት ሄጄ ላገኛት አልፈለግኩም….
እሷም እየተነጫነጨችና በእኔም ልበደንዳናነት እየተደመመች የመዳን ተስፋ ያልነበረውን ወንድሟን ይዛ ወደ ዲላ ሄደች ፡፡ከወር ቡኃላ ሞተ ..አሁንም ተስፋ ሳይቆርጡ እንድቀብረው በእለቱ ደወለው አረዱኝ..፡፡እኔ ግን ብስራት ሆኖ ነው የተሰማኝ፡፡ .. ማስታመም የተጠየፉኩትን ሰው ልቀብረው ፍላጐት የለኝም ብዬ ‹እልመጣም አትጠብቁኝ › አልኮቸው፡፡እዛ እነሱ በሀዘን ላይ በነበሩበት በነዛ የተቀደሱ ቀናቶች እኔ እዚህ ነጭ በነጭ የሀበሻ ቀሚሴን ለብሼ በደስታና ፈንጠዝያ አለሜን በመቅጨት አሳለፍኩ…..
ከዛ ቡኃላ እናቴ ከእኔ ጋር ያላትን ግንኙነት ሙሉ በሙሉ አቆመች… ልጄ አደለሽም ቀብሬ ላይ እናዳትቆሚ › ብላ አዋጅ አስነገረች..ልጄም የእሷ አጋዥ ሆነች፡፡የምልክላትን ብር‹ያአንቺን ሳንቲም ብጠቀም ህርም የወንድሜን ስጋ ይሁንብኝ ›ብላ አሻፈረኝ ብላ ደጋግማ መለሰችልኝ..ይታይህ የተለየ ገቢ የላትም… በትንሽ የአባቴ ጡረታ ነው የምትተደደረው …፡፡እኔው ነበርኩ ጎዶሎዋን የምሞላላት …ሽንቁሯን የምደፍንላት..ግን በቃ ቆረጠች ፡፡..እሷ ብቻ አይደለችም ለልጄ እንኳን በጐን ገንዘብ ልልክላት ብሞክር ‹ከእናቴ ጀርባ ተደብቄ ከንቺ ጋር በመመሳጠር እንድታዝንብኝ ማድረግ አልፈልግም››ብላ እምቢ አለቺኝ፡፡
አይገርምህም እንደእኛ ህዝብ መጥፎ የለም…አንተን በፀፀት ለማሰቃየት ሲል የህይወት ዋጋም ቢሆን ከመክፈል ወደኃላ አይልም…..ሌላው ይቅር ከሞተ ቡኃላ እንኳን ይቅር ሊልህ ስለማይፈልግ‹ቀብሬ ላይ እንዳትቆም› ብሎ ይገዝትሀል..ቢያንስ እስከመጨረሻው እንዳጣሀው ባወቅክ ጊዜ ቀብሩ ላይ ቁጭ ብለህ ያጠፋሀውንእና የበደልከውን በደል በማሰብና በማልቀስ የሙት መንፈሱን እንኳን ይቅርታ እንዳትጠይቅ…ከዛም በሀሳብ ይቅርታ የተደረገልህ መስሎህ ቀለል እንዳይልህ …ዕድሜህን ሙሉ ደስታን እንደተነጠቅክና ድሮ በሆነ ወቅት የሰራሀውን ስህተት በጫንቃህ እንደተሸከምክ አንተም ወደመቃብር እንድትወርድ ያደርጉሀል…..የገዛ እናትህም አትራራልሀም….ከይቅርታ ይልቅ በቀል ሚቀለን ህዝቦች ነን፡፡ሀገራችን የሀይማኖት ሀገር ነች..ግን አጥፊን በፍቅር ከማከም እና በምክንያት ከመገሰፅ ይልቅ …በማግለል ይበልጥ ማድማት እና በውግዘት በቀለኛ እና ሰው ጠል እንዲሆን በማድረጉ ተክነንበታል…. እኔም የአሁኑ ማንነቴ የዚህ ክፉ ባህል ውጤት የወለደው ነው..፡፡
አቤል የሚሰማቸው ነገሮች ከገመተው በላይ የተወሳሰቡ ሆኖ አገኛቸው‹‹ቆይ ለምን አንዴ በአካል ሄደሽ ለእናትሽ ውሸቱንም ሆነ እውነቱን በመናገር ልታሳምኚያቸው እና ግንኙነታችውን ለማደስ አትሞክሪም››
በዛ ማራኪና ብሩህ ፊቷ ላይ እንባዋ ኩልል እያለ መናገር ጀመረች‹‹እዛ የማልሄድበት ሌላ ምክንያት አለ ›› አለችው ኩማደር መሀሪ ላይ የሰራችው በደል ትዝ እያላት ፡፡እርግጥ ኩማደር መሀሪ የሚባል ሰውዬ እሷን ተከትሎ ዲላን ለቆ እንደወጣ ሰምታለች፡፡ወደየት እንደሄደ አሁንስ የት እንደሚገኝ ማንም አውቃለው የሚላት ሰው አላገኘችም…እሷ ግን እዛው አካባቢ እሷኑ አድፍጦ ሊያጠፋት እየጠበቃት እንደሆነ ትገምታለች…›ነገሩ በተከሰተ ሰሞን ደውሎ ዝቶባት ነበር፡፡ አጭር ዛቻ‹‹.ከዛሬ ጀምሮ የምኖረው አንቺን እስካጠፋ ድረስ ብቻ ነው ››ነበር ያላት፡፡ስለዚህ አይደላም ወደ እዛ ሄዳ …እዚሁም አዲስ አበባ ሆና የስጋት ኑሮ ነው የምትገፋዋ..እና ሌላው ምክንያት ያለችው ባታብራራለትም ምክንያቷ ግን ይሄ ነበር….
አቤል ማልቀሷን እንድታቆም እየተማፀናትና ሉጫ ፀጉሩን በሀሳብ ተውጦ በረጃጅም ጣቶቹ ወደኃላ እየላገ መፍትሄ ያለውን ሀሳብ አቀረበ
‹‹እኔ ለምን ዲላ ሄጄ እናት እና ልጅሽን አላናግራቸውም?››
‹‹እንዴ ምን ብለህ?››.
‹‹የሚባለውን ብዬ እንዲረዱሽ ማድረግ እፈልጋለው…መቼስ አጐትሽን ታሞ መጠየቅም ሆነ ከሞተም ቡኃላ መቅበር ያልፈለግሽበት የራስሽ የሆነ አሳማኝ እውነት ስላለሽ ነው ብዬ አምናለው፡፡እነሱም አንቺን ያኮረፉሽ እና ካንቺ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለማቋረጥ የወሰኑበት የራሳቸው እውነት አላቸው….
ብዙውን ጊዜ ሰዎች ሌላውን ሰው የሚቀየሙት ለራሳቸው እውነት ብቻ ትኩረት በመስጠት የሌላውን ወገን እውነት ጭራሽ ባለማዳመጥ ወይም ትኩረት ባለመስጠት ነው፡፡እንደግለሰብም ሳይሆን እንደሀገርም ቡዙ ነገረችን የምናበላሸው ሁላቸንም ለራሳችን እውነት ያልነውን ብቻ እንዲደመጥልን እና ሁሉም ያንን ተቀብሎ እዲያስተጋባል ስለምንፈልግ ነው….ስለዚህ አንቺም የራስሽ እውነት እንዳለሽ ቢያንስ እነሱም ማሰብ እንዲጀምሩ ማድረግ እችላለው›› አላት
‹‹አይ ቢሆንልህ በህይወቴ በጣም የሚያስደስተኝን ውለታ ዋልክልኝ ማለት ነው ፡፡ግን የሚሳካልህ አይመስለኝም..ምክንያቱም የእኔን እውነት እንኳን ለእነሱ ለእኔም አይገባኝም፡፡››
‹‹ይሁን ግድ የለሽም…. በሚቀጥለው ወር ውስጥ ወደ ዲላ እሄዳለው››አላት ፈርጠም ብሎ፡፡እስከዛ ድርስ ከእናት እና ከልጆ ጋር የምደራደርበትን እውነት እና ሚስጥር ትነግረኛለች ብሎ በመተማን ነበር ይሄንን ቃል የገባላት፡፡
አሁን ሁሉንም ትቶ ሊያጽናናት ፈለገ..የምታረግፈውን እንባ ሊያብስላት …. እና በደንብ ተጠግቷት ወደራሱ ጐተታት፡፡ከንፈሩን ወደከንፈሯ ላከና ተጣበቀባት፡፡በደስታ ተቀበለችው፡፡ስስ ከንፈሯን በወፍራም ከንፈሩ ጐርሶ ይመጠው ጀመር..እሷም ቃተተችለት…..በሶስት ሰከንድ ውስጥ ጋለች፡፡እጆን ወደ ለበሰችው ጅንስ ሱሪ ዚፕ ላከች..ቁልፉን እንደምንም ታግላ ከፈተች…ዚፑን ወደ ታች አንሸራተተች ፡፡ከዛ ወደ ታች መዥርጣ ለማውለቅ መታገል ጀመረች…እሱም ትግሎን ተመልክቶ ያግዛት ጀመረ…

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እን
👍2
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_አስር
:
በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
ታሪካችንን ወደኋላ ስንስበው..-..

አንዳንድ ጊዜ በሆነ አጋጣሚ ፈርሰን ከእንደገና እንሰራለን ..አፍርሰው የሚሰሩን የቅርባችን የሆኑ.. ያመነቸውና በማመናችንም ስነልቦናችንን እምነታችንን፤ ታሪካችንን፤ፍቅራችንን እና ውስጣችንን ሙሉ በሙሉ አሳልፈን የሰጠናቸው ሰዎች ናቸው፡፡እነዛ ሰዎች መልካምና ቅዱስ ከሆኑ ከውስጣችን ያለውን ጥሩነት መዘው በማውጣት ተንከባክበው… አፋፍተው እና አሳድገው ጥሩ ስብዕና… መልካም ልብ እና ብሩህ ማንነት ያለው ሰው አድርገው ይሰሩናል…፡፡ እንዳጋጣሚ ሆኖ በአጠገባችን የነበሩ ሰዎች መጥፎና ጨካኝ ከሆኑ ደግሞ ውስጣችን ጫጭቶ ተደብቆ የነበረውን ክፋት መዞ በማውጣት አውሬነታችንን ያሳድጉልናል ክፋታችንን ብስለት እንዲኖረው አድርገው ከእንደገና ሳጥናኤላዊ አድርገው ይሰሩናል፡፡
መልካም ሰው ከሆንን መልካምነታችን ከተከለለበት ሽፋን ገለጥ ገለጥ አድረገው..ከልባሳችን ፈልቅቀው ያወጡን መልካም ሰዎች እንዳሉ ሁሉ.. ክፍ ሆነንና ከመንገድ አፈንግጠን ከሆነ ለመጥፎነታችን፤ ከሀገር ባህል ለማፈንገጣችን፤ የሞራልን ህግ ለመደርመሳችን.፤ለዓለም ስጋት ለመሆናችን ምክንያት የሆኑ በክፉ ስራ ጐልብተው በክፉ ስራ የተመረቁ ሰዎች ከጀርባችን አሉ..፡፡መሰረታችን የገነቡልን እነሱ ናቸው፤ማንነታችንን የሰሩት እነሱ ናቸው፡፡ እሮዛ ክፉ ሰው አፍርሶ ከእንደገና ከሰራቸው እድለቢሶች መካከል አንዷ ነች፡፡
ሮዝ አዲስአበባ ከገባች 1 ወር አልፎታል፡፡ዲላን ለቃ ለሁለተኛ ጊዜ አዲስ አበባ መኖር በመጀመሯ ደስተኛ ነች፡፡ እርግጥ ከኩማንደር ደረሰ ጋር በተስማማችው መሰረት ሙሉውን ብር በቃላቸው መሰረት አልሰጧትም…ግን አልከፋትም፡፡300ሺ ብር አሸክመዋታል፡፡በዛም ደስተኛ ነች፡፡ይሄ ብር በጥሩ ጊዜ ነው የደረሰላት፡፡ ቢያንስ ሳትዋረድ ከመሀሪ እጅ ሾልካ እንድትወጣ አግዞታል፡፡
አሁን የምትወደውን ስራ ጀምራበታለች..22 አካባቢ ውስኪ ቤት ከፍታለች..ይሄ የዘወትር ህልሞ ነበር፡፡ይሄው ባላሰበችው ቀንና አጋጣሚ ተሳካላት፡፡ግን ሙሉ መረጋጋት አይታይባትም፡፡ ትፈራለች ..መሀሪ በህልሞ ሁሉ እየመጣ በሳንጃ ወግቷ ሲያቆስላት፤ በሽጉጥ ተኩሶ ሲገድላት፤ በገመድ ሸምቅቆ ዛፍ ላይ ሲያንጠለጥላት ነው የሚያድረው…፡፡በተለይ ኩማንደር ደረሰ መጥቷ እሷ ጋር አድሮ ስለመሀሪ የባህሪ ለውጥ በዝርዝር ካስረዳት ቡኃላ ስጋቷ ብሷል…፡፡ሰውን ማናገር እንደተወ..የለየለት ጠጪ እንደሆነ ፤እሱንም ችላ እንደለው…ዲላንም ለመልቀቅ ቅያሪ እየጠየቀ መሆኑን ካስረዳት ቡኃላ በቃ እንደጣረ ሞት ሆኖባታል…..፡፡
አሁን ግን ለጊዜው ያስጨነቃት ሌላ ነገር ነው…አንደኛ የልጆ ነገር፤ሁለተኛም የእናቷ ነገር፡፡
ልጆ ሄለን ከመጣች ጀምሮ አንድ ቀን ብቻ ነው በስልክ ያናገረቻት..ልጆ ቁርጥ ያለ ነገር ነግራታለች.-የዘመናት ጥያቄዋን አጠንክራ ‹የአባቴን ማንነት ልትነግሪኝ ካልሆነ በስተቀር ዳግመኛ እኔን ለማግኘት እንዳትደውይ›› ብላ ቁርጥ ያለውን ውሳኔዋን ከነገረቻት 15 ቀን አልፎል፡፡ እሷ ደግሞ እንደዚህ ጥያቄ መስማት ማትፈልገው..እንደዚህ ጥያቄ ሚቀፋትና ሚያስጨንቃት የለም..፡፡ምክንያም ጥያቄዋን መመለስ አትችልም፡፡..አባቷን ልትነግራት ፍጹም አትችልም…አላውቀውም ብትላትም ልታምናት አልቻለችም፡፡
ሌላው ከእናቷ ጋር የተያያዘ ጉዳይ ነው፡፡ እናቷ አሁን አዲስአበባ ናቸው ያሉት፤ እናቷ እሷን ጥየቃ አይደለም የመጣችው… ፍጹም፡፡ አመጣጧ ወንድሞ ታሞባት ልትጠይቀው ነው፡፡ መንታዋ፡፡ይሄንን ደውላ የነገረቻት እናቷ ነች‹ ነይና አግኚኝ› ብላታለች፡፡ግን እንዴት አድርጋ ነው ጠላቷ ቤት የምትሄደው? እርግጥ አንድ ቀን እሱ ፊት ለፊት ለመቅረብ ዕቅድ ነበራት ..ያ ቀን ግን አሁን እልነበረም የመጨረሻ ዝግጅቷን ካጠናቀቀች ቡኃላ ነበር እሱ ፊት መቅረብ ምትፈልገው..ልትገድለው በወሰነች ቀን፡፡
አሁን ግራ ገብቷታል፡፡እናቷን ውጭ እንዲገናኙ ብትጠይቃትም በጣም ነው ያንዘራዘራት ስለዚህ ምርጫ ስለሌላት ለመሄድ ወስናለች፡፡ የተንጣለለ የግንብ አጥር ዙሪያውን በአደገኛ ሽቦ የተከበበ ግቢ ደረሰች፡፡መጥሪያውን ተጫነችው፡፡ልክ የሲኦል በራፍ እንደምታንኰኰ እና ሳጥናኤል መንበር ፊት እንደምትቀርብ ሆኖ ነው የተሰማት፡፡በራፉ ተከፈተ ፡፡አንድ ወገቡ ጐብደድ ያለ ዘበኛ ነበር የከፈተላት
‹‹አቤት የእኔ ልጅ..ምን ፈለግሽ?››
‹‹የአቶ ክንፈ ቤት ነው አይደል?››
‹‹ለምን ፈለግሽው ልጄ? ጌታዬ እኮ ሰው ማግኘት ካቆሙ ወራት አለፋቸው ታመው አልጋ ይዘዋል››
‹‹ጥሩ ነው››በሽታ በለገሰው ስቃይ ተደስታ
ሽማግሌው ደነገጡ‹‹ምኑ ነው ልጄ ጥሩ?››
‹‹አይ እኔ ሰው አይደለውም ማለቴ ነው››
‹‹በስመአብ በይ ልጄ..ሰውማ ሰው ነሽ እንጄ …ለዛውም ወርቅና ቆንጂዬ ልጅ››
‹‹ማለቴ እዚህ ልታሰስታምመው የመጣችው እህቱ እናቴ ነች እሷ ደውላኝ ነው፡፡››
‹‹እንዴ አጐትሽ ነዋ…››
‹‹መሰለኝ››
‹‹ወይ ልጄ አፈር በሆንኩ… ግቢ ግቢ››በራፉን ሰፋ አድርገው ከፈቱና እንድትገባ ገለል አሉላት፡፡ገባች፡፡ማራኪ የታዳጊነት ዕድሜዋን ያሳለፈችበትን ጊቤ ስትቃኝ ትዝታዋ ተቀሰቀሰባት፡፡ ..የተከለቻቸው ችግኞች..ያሳደገቻቸው አበቦች… የጥዋት ፀሀይ ትሞቅበት የነበረበት ስፋራ…ትዝታዋን እያጠነጠነች ሳሎን ገባች ማንም አልነበረ..ቁጭ አለች፡፡አብዛኛው ነገሮች እሷ በነበረችበት ጊዜ እነደነበሩ ናቸው..ይሄ ቤት ብዙ ሳቅ የሳቀችበት…ብዙ ደስታ የተደሰተችበት..ብዙ ህልም ያለመችበት ቤት ነው.፡፡በተቃራኒውም ማንነቷን ያጣችበት ፤ህልሟ የጨነገፈበት፤ተስፋዋ የወደመበት፤የህይወት መስመሯ የተሰነካከለበት ቤት ነው፡፡ከልጅነት የዕድሜ ክልል ሳትወጣ የልጅ እናት የሆነችበት ቤት ነው፡፡
‹‹እኔስ ቀረሽ ብዬ ነበር››እናቷ ናቸው ከውስጠኛው ክፍል ወደ እሷ እየመጡ የተናገሩት
‹‹እንዴ እማዬ ሰላም ነሽ?››ከቀመጠችበት ተነሳችና ተሳሳሙ ወደ መቀመጫዋ ተመልሳ ልትቀመጥ ስትል
‹‹እንዴ ነይ እንጂ አጐትሽን አናግሪው››
‹‹አጐትሽን? ››
‹‹ ምነው አዎ አጐትሽን ..ምነው ዛሬም ድረስ የተቀየመሸ መስሎሽ ነው አይደል…?በየቀኑ ያንቺን ስም ሳያነሳ አይውልም…በጊዜው እኔ በስነ ስርዓት ብከታተላት እና ብቆጣጠራት ኖሮ ለእርግዝና አትጋለጥም ነበር የእኔ ጥፋት ነው እያለ ቃላል አይፀፀትም››
‹‹በእውነት ..እንዴት ተፀፅቷል››
‹‹እያሾፍሽ ነው..?በይ ነይ አሁን አናግሪው›› ብላ እናትዬው ቀድማ መራመድ ቀጠለች፡፡ ፈራ ተባ እያለች ተከተለቻት፡፡ ልክ መኝታ ቤቱ በራፍ ጋር ሲደርሱ ድንገት የእናትዬውን ክንድ ጨምድዳ ያዘቻት፡፡ እናትዬው ደንግጣ ‹‹ምነው ፈራሽ እንዴ?››አለቻት
‹‹አይ አልፈራውም ግን ብቻዬን ብገባ ደስ ይለኛል››
እናትዬው እንደማሰብ አለችና‹‹ ጥሩ..እኔ እንደውም ማድቤት ስራ እየሰራው ነበር… መጣው ግቢ››ብላት ጥላት ሄደች፡፡
ሮዝ በራፉን ገፋ አድርጋ ገባች፡፡ሰፊው ባለ 1.80ሜ ሞዝቦልድ አልጋ ላይ ሟምቶ እና ሳስቶ የተዘረጋ አጐቷ ወደ ውስጥ የሰረጐዱ አይኖቹን እያቁለጨለጨ ወደ እሷ ተመለከተ..፡፡በዝግታ ተጠጋችና ስሩ ስትደርስ ቆማ ወደታች አዘቅዝቃ ታስተውለው ጀመረች
.‹‹ሮ..ዝዬ መጣ..ሽ?››አላት በተጐተተ ቃላት
‹‹አንተ እኔስ ገና ሞተህ ሲኦል ከገባህ ቡኃላ ቅጣትህን ምታገኘ ይመስለኝ ነበር..ለካ አንዳንዴ ዘንድሮም እግዚያብሄር ፍርዱ ፈጣን ነው ያ ሁሉ ሰውነትህ እንዲህ ይርገፍ..!ያን የመሰለው መልክህ እንዲህ ይክሰም..አጽምህ ብቻ እኮ ነው ያለው››
ዝም ብሎ እንባዎቹን እያረገፈ ዓይኖቹን እያቁለጨለጨ ምታደርገውን ይከታተላል… የምትለውን ይሰማል
👍31
ሮዝ ውስጣዊ ደስታ ተሰማት..እርካታ፡፡የበላይነት፡፡ ልክ አልኮል ሲጋት አድሮ ጥዋት ሲነሳ የሚጠጣው እርጐ አንደተሰጠው ሰው..ወደ ኃላ ተመለሰችና የመኝታ ቤቱን በራፍ ከውስጥ ቆለፈችው እና ወደ እሱ ተጠጋች…ምን እያደረገች እንደሆነ ግራ ገብቶታል..‹‹ልገድልህ ነው››አለችው ፍርጥም ብላ
‹‹ምኔን ትገይኛሽ..ደግሞም እንዲሁ ሰበብ እሆንብሻለው እንጂ በራሴው ጊዜ በቅርቡ መሞቴ አይቀርም››
‹‹አይ እንደዛማ አይሆንም….አንተን ለመግድ ለአመታት ሳቅድና ስመኝ ቆይቼም እንዲህ አትሸውደኝም…መሞት ያለብክ በእኔ እጅ ነው››
‹‹እኔ ገድለሽ በእስር እንዳትሰቃይ ብዬ እኮ ነው››አላት በቅርቡ እንደሚሞት በሀኪም የተነገረው እና እራሱም እንደሚሞት የተሰማው ቢሆንም አሁን ግን ፈራ ..ለምን እንደሆነ ባያውቅም ፈራ
የለበሰውን ብርድልብስ ገፈፈችውና ባዶውን አስቀረችው ፡፡የለበሰው ነጭ ቢጃማ ከሰውነቱ ጋር ተጣብቋል‹‹በስመአብ የምትመስለውን በመስታወት አይተሀዋል..?የድርቅ ማስተዋወቂያ እኮ ነው ምትመስለው…ይሄን ሁሉ ንብረት አሁን ይዘኃው ልትሞት ነው?››
‹‹ንብረቱ የልጃችን ነው?››አላት
‹‹አንተ!! ደግሞ አፍህን ሞልተህ የልጃችን ትላለህ? ትንሽ አፍህን አይመርህም ››አለችና አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠች..‹‹ልጃችን ነው ያልከው..?›አለችና ቢጃማ ሱሪው ወደታች ጐትታ ከወገብ በታች ዕርቃኑን አስቀረችው…‹አየህ ያ ሁሉ ቅንዝርህ ዛሬ እንዴት እንደሚያስጠላ… እንትንህ እራሱ ኩምሽሽ ብላ ወደ ውስጥህ ገብታ ጠፍታለች እኮ…!!!››እጆን ላከችና ጨበጠችው አጥብቃ ጨመደደችውና ጠመዘዘችው…አጐተዋ የስቃይ ሲቃ አሰማ… አይኖቹ ከጉድጐዶቹ ውስጥ እንዳሉ ፈጠጡ‹‹አየህ በወቅቱ ይሄ ዕቃህ ነው እኔነቴን የበታተነው…ህይወቴን ያጨላለመው በወቅቱ ከአቅሜ በላይ ነበር ..ከህሊናዬም በጣም የራቀ፤አሁን ግን እየው እሲት እንዴት እንደከሰመ››ያዝ ለቀቅ እያደረገች አሰቃየችው፡፡
በዚያን ጊዜ በራፍ ተንኮኮ ‹‹ሮዝ ክፈቺ እስቲ የሚቀምሰው ነገር ልስጠው››
‹‹እሺ እማ መጣው››አለችና ጐትታ ያወቀችውን ቢጃማ ሱሪውን መልሳ አለበሰችው፡፡ ብርድልብሱን መልሳ አለበሰችውና‹‹ስማ አንተ ሳጥናዬል ልሞት ነው ብለህ ስለልጄ አንድ ነገር ትንፍሽ ብትል ወየውልህ..፡፡ደግሞ በሳላም እሞታለው ብለህ ፈጽሞ አታስብ… በቅርብ ተመልሼ እራሴው ነኝ አሰቃይቼ የምገድልህ ..አይ እንደውም አልገድልህም በቁምህ ነው ጫካ ወስጄ ጥዬህ አውሬዎች ቦጫጭቀው እንዲበሉህ የማደርገው››አለችና ለእናትዬው በራፉን ልትከፍት ተንቀሳቀሰች..

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
#ከ ‹‹ፈሮግራምህ›› #ውልፍት_የለም !

አንሾ ባልታወቀ ምክንያት የምትወደው ባሏ አባተ ጋር ትጣላለች ,,,,,እናም ኮብልላ ወላጆቿ ቤት ታድራለች ! በበነጋታው የአገር ሽማግሌወች ባልና ሚስትን ሊያስታርቁ ሽምግልና ይቀመጣሉ !
‹‹ ችግርሽ ምንድነው ?››
‹‹ምንም››
‹‹እንዴት ያለምንም ችግር ትዳርሽን ታፈርሻለሽ ››
‹‹ በቃ አልፈልግም ››
‹‹እኮ ለምን ?›› አሉ ሽማግሌወች በማግባባት አንሾ ስትፈራ ስትቸር አንዲት ነገር ተናገረች ‹‹ አሱ ሰው አይደለም ዝንጆሮ ነው ›› ሽማግሌወቹ ገባቸው ! ባሏ እንደዝንጆሮ ወሲብ ያበዛል አልቻለችውም ማለት ነበር ትረጉሙ…. እናም ሽማግሌወቹ ጉዳዩን በዝርዝር እንድታስረዳቸው ጠየቁ… እ,ሷም አንዴ ከአፏ ወጥቷልና በዝርዝር ጉዳዩን ታስረዳ ጀመረ !
‹‹ እንደው በኔ የደረሰ አይድረስባችሁ … ባለቤቴ ሳያገባኝ በፊት ጎበዝ ገበሬ …. አገር ያወቀው ጀግና ነበር ታውቃላችሁ መቸስ ….ከተጋባን ጀምሮ መሬቱ ሁሉ ጦም አደረ በሬወቹ እንደተጠመዱ ትቷቸው ይመጣና እኔን ይጠምደኛል …. ሌሊት ወገቤ አያርፍ እግሬ አይገጠም ጧት በግድ ተነስቸ ያዘጋጀሁትን ቁርስ ቀመስ አድርጎ ይተውና ወደመደቡ መጎተት ነው ….ውሃ ቀድቸ ስመለስ እንስራየን አውርዶ ወዲያ ይወረውርና ‹ያዥ እንግዲህ › ነው … አልቻልኩም በዛብኝ ምነው ሸዋ ! ›› አለችና ሽማግሌወቹ ፊት አለቀሰች ! ሽማግሌወቹም ችግሯን ስለተረዱ እዛው ተቀምጦ ጉዱን የሚሰማውን ባሏን ጠሩና መከሩት
‹‹አባተ ››
‹‹አቤት አባቶቸ ›› አለ እየተቅለሰለሰ
‹‹እንግዲህ የተባለውን ሰምተሃል እውነት ነው ሃሰት ? ››
‹‹ኧረ ሃቅ ነው አባቶቸ ….›› ሲል አመነ
‹‹ ጥሩ እንግዲህ ጥፋት አይተንብሃል በል አሁን የምንመክርህን ስማ ›› አሉና ሽማግሌወቹ ተመካክረው በአንድ ወግ አዋቂ ሽማግሌ በኩል እንዲህ አሉት
‹‹ እንግዲህ አባተ <እንትን > እንደሆነ ዝም ብለው ቢውሉበት ቁርስ አይሆን ምሳ ርስት አይሆን ሃብት …. እየናፈቀ ሲገኝ ነው ደጉ …ይሄው አረጀንበት ከልጅነት እስከእውቀት ኖርንበት እሱ እንደሆን እያደር አዲስ ነው ከምን እንደሰራው አንድየ ይወቀው …..እና አሁንም አንተም ሚስትህን አንሻን እንዳታማርራት በ ‹ፈሮግራም › እንዲሆን ወስነንበሃል ›› ሲሉ አስረዱ
‹‹ እሽ አባቶቸ እንዳላችሁ ….ግ…..ን ‹ፈሮግራሙ› እንዴት እንዴት ነው ›› አለ አባተ
‹‹ እንግዲህ ፈሮግራሙ እንዲህ ነው …. ቀን ቀን እቤት ድርሽ ሳትል እርሻላህ ላይ ትውልና ማታ ጀምበር ሲያዘቀዝቅ ከብቶችህን አስገብተህ ስታበቃ አንሾም ናፍቃህ ትውል የለም …..አንደዜ ! ….ደሞ ራት ተተበላ በኋላ ኩራዝ ጠፍቶ ጋደም ስትሉ ….አንደዜ ! ወደንጋጋቱ ላይ ዶሮ ሲጮህ ደሞ አንደዜ ! ሶስት ሃቅህ ነው !›› አሉት
አባተ ቅር እያለው እንዲህ አለ ‹‹ እንደ…..ው ኣባቶቸ ምክራችሁ ጥሩ ነበር ግ…..ን እነደው …. ለጠራራውም ለውሃ ጥሙም ቀን ላይ አንደዜ ብትጨምሩልኝ ›› ሲል ጠየቀ
አንሾ በተራዋ ‹‹ የዶሮ ጩኸቱን ብታነሱልኝ ምናለ …. ሁለቴ ካገኘ ምን አነሰው ›› ስትል ቅሬታዋን አቀረበች ! ሽማግሌወቹ ግራ ቀኙን አድምጠው ‹‹ አንሾ አንችም አትሰስች ….አንተም ከ ‹ፈሮግራምህ› ውልፍት የለም ! ከተሜው ሁሉ እንዲሁ ነው የሚያረግ ›› አሉና በውሳኔያቸው ፀኑ !
አንሾና አባተም እርቅ አውርደው ወደቤታቸው ሄዱ ! ልክ እቤታቸው ሲደርሱ ጀምበር አዘቅዝቆ ስለነበር አባተ እየተጣደፈ አንሾን ወደመደቡ ጎተታት …. አንሾም ተጣልተው ስለቆዩ ናፍቋት ስለነበር አልከፋትም ኧረ እንደውም ደስ አላት !
‹‹ አንድ በል ቁጥር እነዳትስት ›› አለች ቀሚሷን እያጠለቀች ! አፍታ ሳይቆይ አባተ አንሾ አማረችው ! አለፍ ስትል ሳብ አደረገና እነሆ ! ሁለት ! ገና እራት ሳይቀርብ አንሾ ጉድ ጉድ ስትል ጠይም ፊቷ በምድጃው እሳት ወጋገን ወርቅ መስሎ ታየው አባተ አላስችል አለው በቃ ሳብ አደረጋና ሶስተኛውን ሃቁን አነሳ !
እራት ቀርቦ በሉና ጋደም እንዳሉ አባተ የአንሾ አርቲ እና አሽኩቲ ጠረን አቅሉን ነሳው ! ሽማግሌወች የወሰኑለትን ኮታ ደግሞ ጨርሷል እናም በጨለማው ውስጥ ቀስ ብሎ እንዲህ አለ ‹‹አንሾ ››
‹‹ምን ፈለክ…..የዛሬውን ድርሻ ሶስትህን ጨርስሃል ነገር ትፈልገኝና ውርድ ከራሴ ›› አለች አንሾ በቁጣ
‹‹ እንደው አፈር ትሆንልሽ …..ተነገው አንድ አበድሪኝ አንሾዋ ›› አላት ያልሆነ ቦታ እየደባበሳት .....አንሾ አሰብ አደረገች እሽ እንዳትል ኩራቷ ያዛት እምቢ እንዳትል የአባተ እጅ ቀልቧን ወስዶታል እናም እንዲህ አለች ‹‹ ምን የነገውን አበዳደረህ የትላንቱስ ሶስቱ መች ተነካ ›› ትላንት ተጣልተው አብረው አላደሩም !!
ወደቁም ነገራችን ስንመለስ በባልና በሚስት እንዲሁም በፍቅረኞች መሃል ለሚፈጠሩ ችግሮች መፍትሄው ሶስተኛ ወገን ሳይሆን ፍቅር ራሱ ነው #ፍቅር_ብቻ !!!!
👍3