#ራሴው_ማበዴ_ነው
:
#ክፍል_ስምንት
:
✍ደራሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
:
...በሰላሳ አንድ ዓመቴ ማንም ወንድ ነክቷት የማታውቅ ድንግል ሴት መሆን የሚያኮራ ነገር ይሁን የሚያሳፍር አላውቅም (‘ድንግል’ የሚለውን ቃል እጠላዋለሁ ቃሉን እንጂ ነገርየውን አይደለም። በእርግጥ ነገርየውንም ልውደደው ልጥላው እርግጠኛ አይደለሁም። ቃሉ ግን የሆነ አፍ ላይ ሲባል ራሱ ድንግል፣ ደናግል፣ ድንጉላ……… ድንዝና አለበት።) እውነታው እግሮቼ መሃል ካለ ነገር ድፍንነት ወይ ጠባብነት በላይ ዓይኖቼን የማያስነቅሉ የኔን ትኩረት የሚሹ አሳሳቢ የዕለት ተዕለት ጉዳዮች የከበቡኝ ሴት ሆኜ በመኖሬ ትርጉሙም ጣዕሙም አይገባኝም። ድንገት እንኳን በሀሳቤ ሽው ካለ የማልም የነበረው አቅፎኝ የሚያድር የሆነ የማላውቀው ፈርጣማ ወንድ ሰውነት ነው። ማቀፍ ብቻ!! ሌላውን ‘ፓኬጅ’ አላስበውም። እኔ እና እማዬ ብቻችን መኖር የጀመርን ዓመት እማዬ ሲነሳባት ለሊቶቹ ይረዝሙብኛል። ምን እንደምፈራ አላውቅም ግን ስለምፈራ ዓይኔን አልከድንም። ጨለማው፣ ኮሽታው፣ ፀጥታው…… ሁሉም ያስፈራኛል። እጅግ ጥልቅ ፍርሃት እፈራለሁ። ድፍረት የፍርሃት ተቃራኒ አይደለም። የፍርሃት ሌላ ተቃራኒ ሊኖረው ይገባል። ምክንያቱም ድፍረት አለመፍራት አይደለማ። ይልቁንስ ድፍረት ፍርሃትን መጋፈጥ ነው። ድፍረት ፍርሃት እንዳያስቆምህ እየተንቀጠቀጥክም ሆነ እየዳህክ በፍርሃትህ ጫካ ውስጥ ሰንጥቀህ ማለፍ ነው።
እማዬ እና አባቴ ከተለያዩ በኋላ ከታላቅ እህቷ (ከአክስቴ) ጋር ነበር የምንኖረው። የአስራ ሁለተኛ ክፍል ትምህርቴን ጨርሼ ውጤት እየጠበቅኩ በነበረበት ክረምት አክስቴ ትኖር የነበረበትን ትልቅነቱ እና ፀጥታው የሚያስፈራ ቤቷንና ቢያንስ በዓመት ሶስቴ እብደቷ የሚነሳባት እህቷን (እናቴን) አስተዳድሪ ብላኝ አውስትራሊያ ከሄዱ ከእኔ እድሜ በላይ ያስቆጠሩ ቤተሰቦቻቸውን ተቀላቀለች። ከእርሷ በቀር ሀገር ውስጥ የቀረ የቅርብ ዘመድ ያልነበራት እናቴ ብዙም ሳትቆይ የበረራ ቁጥሯን መቁጠር ጀመረች። እንኳን እሷን ላረጋጋት እኔ ከርሷ ብሼ እጅና እግሬ እየተንቀጠቀጠ አለቅሳለሁ። መድሃኒቷን በስቃይ ወስዳ ስታንቀላፋልኝ። እያንዳንዱ የቆዳዬ ነጠብጣብ ቀዳዳ ፍርሃትን እየማገ ወደሰውነቴ ሲነዛው እየተሰማኝ ተስፋ ላለመቁረጥ እና ላለመውደቅ እታገላለሁ። ለፍርሃት እጅ ላለመስጠት!! ያ ነው ድፍረት ማለት። መታገል!! በነዚህ ጊዜያት ነበር በእቅፉ የሚከልለኝ ሰውነት የምመኘው!! ሰውነቱን እንጂ ሰውየውን አልሜ አላውቅም። ሰፊ ትከሻ፣ ሰፊ ደረት፣ ፈርጣማ ጡንቻ፣ ረዥም ቁመት…… ለውበት ሳይሆን ከፍርሃቴ ለመከለያ፤ ለስሜት ሳይሆን ለመደበቂያ፤ ለመፈንጠዣ ሳይሆን ለመወሸቂያ… …ከአንገቱ በላይ ባይኖረውም አልያም ምንም ቢመስልም አስቤው አላውቅም።
“ራሁ? እየሰማሽኝ እኮ አይደለም። ምን ሆነሻል? ከቅድም ጀምሮ ላጫውትሽ እሞክራለሁ። ከእኔ ጋር አይደለሽም።”
“ይቅርታ ፍትህ ትንሽ ራሴን አሞኛል።”
“ምን ላድርግልሽ? ሀኪም ቤት ልውሰድሽ? (እጁን ግንባሬ ላይ አድርጎ ማተኮሴን ያረጋግጣል። በጭንቅላቴ ንቅናቄ መሄድ ያለመፈለጌን ነገርኩት።) እሺ በቃ ነገ ይደርሳል ነገ አወራሻለሁ።እረፍት አድርጊ!” ብሎኝ ተነሳ። ምን አስቤ እንደሆነ እንኳን ለመረዳት ከራሴ ተማክሬ ያላደረግኩትን ድርጊት ተስፈንጥሬ እጁን ይዤ አሰቆምኩት። ቀጥዬ ለምን እንዳስቆምኩት የምሰጠው ምክንያት አልነበረኝም።
“ወዬ? ምን ላድርግልሽ? እንዲህ አድርግልኝ በይኝ። እ ራሁ? (ተመልሶ ተቀምጦ ይዞ ያስቀረውን እጄን እያሻሸ ፣ዓይን ዓይኔን እያየ እና ሁሉም የስሜት ህዋሳቶቼ በሚገባቸው ድምፅ ተንሾካሾከ።) ልታወሪልኝ የምትፈልጊው ነገር አለ? እ? እሺ እንዳድርልሽ ትፈልጊያለሽ?”
“አይይይ አልፈልግም።” አልኩት። አጠገቤ እንዲሆን እኮ እፈልጋለሁ። ሲነካኝ ግን እበረግጋለሁ። እጆቼን ሲያሻሽ ፣ ቅድም እንዳደረገው አንገቴ ስር ሲስመኝ ፣ ዓይኖቼን በሚለማመጡ ዓይኖቹ ሲያያቸው…… መሸሽ እፈልጋለሁ። እንዲህ ሲያደርግ የሚሰማኝን ስሜት ስለምጠላው አይደለም። ስለምወደው እንጂ። ነገር ግን ደስ የሚለኝ አዲስ ስሜት ያስፈራኛል። ሁሌም ቢሆን ያልተለማመድነው አዲስ ነገር፣ አዲስ ሀሳብ፣ አዲስ ስሜት……… ብቻ አዲስ ልምድ መጠኑ ቢለያይም ፍርሃት ያጅበዋል። ምክንያቱ ደግሞ ውጤቱ ከግምት ያለፈ ማረጋገጫ የለውም። ለዚህ ይመስለኛል የብዙ ሰዎች ኑሮ የተለመደ እና የተደጋገመ የሚሆነው። ከአዲስ ነገር ጋር አብሮ ብልጭ የሚለውን ፍርሃት መጋፈጥ የቻሉ ጥቂት ደፋሮች ለአለማችን አዳዲስ ሀሳቦች እና ፈጠራዎች አበርክተዋል።
“እሺ እኛ ቤት እንሂድ? ከካስዬ ጋር ስትጫወቺ ይለቅሻል። እንሂድ?”
“አይ… … ስለትዝታ የደረስኩበት ነገር አለኝ አላልክም ነበር? እሱን እንድትነግረኝ ነው።” የሚል ምክንያት ነበር የመጣልኝ
“ስለትዝታ ልትጠይቂኝ ነው እጅሽ የሚያልብሽ?( ያላበው መዳፌን በእጁ እየጠረገ ያደርቃል። ይሄኔ እኮ ድምፅ ከጆሮ ውጪ በሌላ የስሜት ህዋስ እንዴት ይተረጎማል? ብሎ የሚጠይቅ አላዋቂ አይጠፋም። አሁን ፍትህ እያወራ ያለበት ባለጣዕም ድምፅ ቀላል ይጣፍጣል?) ስለትዝታ ልትጠይቂኝ ነው ዓይንሽ የሚሸሸኝ? (ይሄን ያለበት ድምፅስ ቀላል የሚያውድ መዓዛ አለው?) ስለትዝታ ልትጠይቂኝ ነው ጉንጭሽ የቀላው? (ይሄኛው ቀለማት አሉት። ዓይን የሚይዝ የቀለም ስብጥር) ስለትዝታ ልትጠይቂኝ ነው ቃላት ለማውጣት ያማጥሽው?( ይሄኛው እንደሚያባብል የውሃ ዳር ንፋስ በቆዳዬ ላይ ሽውውውው እያለ ይዳብሰኛል።)” ጭራሽ የማወራው ጠፋብኝ። በዛው ድምፅ ቀጠለ
“ስለስራ ስታወሪ ዓይኖችሽ ዓይኖቼን ያሳድዳሉ ፣ አንገትሽን ቀና አድርገሽ የምትናገሪው ተፅፎ የተሰጠሽ አይነት ‘articulated’ ነው፣ በጥያቄሽ ብዛት እኔን ያልበኛል። …… ንገሪኝ ምን ልትዪኝ ነበር እጄን የያዝሽኝ?” (ይሄንን ድምፅ ጥፍሬ እና ፀጉሮቼ እንኳን ላይሰሙት አይችሉም።)
“ምንም!! ምንም የምልህ ነገር ኖሮኝ አይደለም። …… በቃ እንድትቆይ ብቻ ፈልጌ ነው።”
“እሺ (ያልከለለውን ፀጉሬን ወደኋላ እያደረገ) እሺ እንድቆይልሽ እስከምትፈልጊው ጊዜ ሙሉ የእድሜዬን ቁጥርም ቢሆን እቆይልሻለሁ። ምን እያደረግኩልሽ እንድቆይ ነው የምትፈልጊው?”
“አላውቅም!! ፍትህ የተሰማኝን ስለነገርኩህ እንዳፍር እያደረግከኝ ነው።” ስለው ፈገግ ማለቱን ሳላየው በምን አወቅኩ? ምራቄን እየደጋገምኩ በሚያስተጋባ ጉሮሮዬ የምውጠው ምን ሆኜ ነው? አፍንጫዬ ሳይቀር የሚያልበኝስ?
“እሺ!!” ብሎኝ እጄን ለቀቀኝ። ከሶፋው ላይ ትንሽዬዋን ትራስ አንስቶ እኔ ከተቀመጥኩበት በተቃራኒ ጥግ ተቀመጠ።ትራሷን ጭኑ ላይ ካስቀመጠ በኋላ በእጁ እየመታ ጠቆመኝ። ጀርባዬን ሰጥቼው እግሬን ሰቅዬ እሱን ተንተርሼ ተጋደምኩ።
“ፊትሽን አትከልዪኝ። ወደዚህ ዙሪና ከፈለግሽ ዓይንሽን ጨፍኚ።” አለኝ ቀጠለና። እንዳለኝ አደረግኩ። ዓይኔን ግን አልጨፈንኩም። ፀጉሬን በጣቱ እያበጠረ ለደቂቃዎች ካለምንም የቃላት ልውውጥ ከቆየን በኋላ።
“እንቅልፍሽ ከመጣ መተኛት ትችያለሽ።” አለኝ
“ከዛስ? አንተስ?”
“ያላደለው ጨለማ ላይ አፍጥጦ ያድር የለ? አንቺን የመሰለ ውበት ላይ አፍጥጦ ማደር ተገኝቶ ነው? ውብ’ኮ ነሽ ካስዬ ይሙት! (እጄን የማስቀምጥበት አጥቼ አቅበዘበዝኩት።) እፍረትሽ መጣ?” ብሎኝ ሳቅ ሲል በጨረፍታ አየሁት።
” አንዳንድ ነገር ሳጣራ ነበር። ምን ያህል እንደሚጠቅመኝ ባላውቅም አንዳንድ መረጃዎች ……”
“እስኪ ንገረኝ።”
“የሟች ታሪክ ትዝታ ካለችው የራቀ ነው። ሟች የሰውየው ፍቅረኛ አልነበረችም። ከዚያ ቀን በፊትም ተያይተው አያውቁም። የምትማርበት
:
#ክፍል_ስምንት
:
✍ደራሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
:
...በሰላሳ አንድ ዓመቴ ማንም ወንድ ነክቷት የማታውቅ ድንግል ሴት መሆን የሚያኮራ ነገር ይሁን የሚያሳፍር አላውቅም (‘ድንግል’ የሚለውን ቃል እጠላዋለሁ ቃሉን እንጂ ነገርየውን አይደለም። በእርግጥ ነገርየውንም ልውደደው ልጥላው እርግጠኛ አይደለሁም። ቃሉ ግን የሆነ አፍ ላይ ሲባል ራሱ ድንግል፣ ደናግል፣ ድንጉላ……… ድንዝና አለበት።) እውነታው እግሮቼ መሃል ካለ ነገር ድፍንነት ወይ ጠባብነት በላይ ዓይኖቼን የማያስነቅሉ የኔን ትኩረት የሚሹ አሳሳቢ የዕለት ተዕለት ጉዳዮች የከበቡኝ ሴት ሆኜ በመኖሬ ትርጉሙም ጣዕሙም አይገባኝም። ድንገት እንኳን በሀሳቤ ሽው ካለ የማልም የነበረው አቅፎኝ የሚያድር የሆነ የማላውቀው ፈርጣማ ወንድ ሰውነት ነው። ማቀፍ ብቻ!! ሌላውን ‘ፓኬጅ’ አላስበውም። እኔ እና እማዬ ብቻችን መኖር የጀመርን ዓመት እማዬ ሲነሳባት ለሊቶቹ ይረዝሙብኛል። ምን እንደምፈራ አላውቅም ግን ስለምፈራ ዓይኔን አልከድንም። ጨለማው፣ ኮሽታው፣ ፀጥታው…… ሁሉም ያስፈራኛል። እጅግ ጥልቅ ፍርሃት እፈራለሁ። ድፍረት የፍርሃት ተቃራኒ አይደለም። የፍርሃት ሌላ ተቃራኒ ሊኖረው ይገባል። ምክንያቱም ድፍረት አለመፍራት አይደለማ። ይልቁንስ ድፍረት ፍርሃትን መጋፈጥ ነው። ድፍረት ፍርሃት እንዳያስቆምህ እየተንቀጠቀጥክም ሆነ እየዳህክ በፍርሃትህ ጫካ ውስጥ ሰንጥቀህ ማለፍ ነው።
እማዬ እና አባቴ ከተለያዩ በኋላ ከታላቅ እህቷ (ከአክስቴ) ጋር ነበር የምንኖረው። የአስራ ሁለተኛ ክፍል ትምህርቴን ጨርሼ ውጤት እየጠበቅኩ በነበረበት ክረምት አክስቴ ትኖር የነበረበትን ትልቅነቱ እና ፀጥታው የሚያስፈራ ቤቷንና ቢያንስ በዓመት ሶስቴ እብደቷ የሚነሳባት እህቷን (እናቴን) አስተዳድሪ ብላኝ አውስትራሊያ ከሄዱ ከእኔ እድሜ በላይ ያስቆጠሩ ቤተሰቦቻቸውን ተቀላቀለች። ከእርሷ በቀር ሀገር ውስጥ የቀረ የቅርብ ዘመድ ያልነበራት እናቴ ብዙም ሳትቆይ የበረራ ቁጥሯን መቁጠር ጀመረች። እንኳን እሷን ላረጋጋት እኔ ከርሷ ብሼ እጅና እግሬ እየተንቀጠቀጠ አለቅሳለሁ። መድሃኒቷን በስቃይ ወስዳ ስታንቀላፋልኝ። እያንዳንዱ የቆዳዬ ነጠብጣብ ቀዳዳ ፍርሃትን እየማገ ወደሰውነቴ ሲነዛው እየተሰማኝ ተስፋ ላለመቁረጥ እና ላለመውደቅ እታገላለሁ። ለፍርሃት እጅ ላለመስጠት!! ያ ነው ድፍረት ማለት። መታገል!! በነዚህ ጊዜያት ነበር በእቅፉ የሚከልለኝ ሰውነት የምመኘው!! ሰውነቱን እንጂ ሰውየውን አልሜ አላውቅም። ሰፊ ትከሻ፣ ሰፊ ደረት፣ ፈርጣማ ጡንቻ፣ ረዥም ቁመት…… ለውበት ሳይሆን ከፍርሃቴ ለመከለያ፤ ለስሜት ሳይሆን ለመደበቂያ፤ ለመፈንጠዣ ሳይሆን ለመወሸቂያ… …ከአንገቱ በላይ ባይኖረውም አልያም ምንም ቢመስልም አስቤው አላውቅም።
“ራሁ? እየሰማሽኝ እኮ አይደለም። ምን ሆነሻል? ከቅድም ጀምሮ ላጫውትሽ እሞክራለሁ። ከእኔ ጋር አይደለሽም።”
“ይቅርታ ፍትህ ትንሽ ራሴን አሞኛል።”
“ምን ላድርግልሽ? ሀኪም ቤት ልውሰድሽ? (እጁን ግንባሬ ላይ አድርጎ ማተኮሴን ያረጋግጣል። በጭንቅላቴ ንቅናቄ መሄድ ያለመፈለጌን ነገርኩት።) እሺ በቃ ነገ ይደርሳል ነገ አወራሻለሁ።እረፍት አድርጊ!” ብሎኝ ተነሳ። ምን አስቤ እንደሆነ እንኳን ለመረዳት ከራሴ ተማክሬ ያላደረግኩትን ድርጊት ተስፈንጥሬ እጁን ይዤ አሰቆምኩት። ቀጥዬ ለምን እንዳስቆምኩት የምሰጠው ምክንያት አልነበረኝም።
“ወዬ? ምን ላድርግልሽ? እንዲህ አድርግልኝ በይኝ። እ ራሁ? (ተመልሶ ተቀምጦ ይዞ ያስቀረውን እጄን እያሻሸ ፣ዓይን ዓይኔን እያየ እና ሁሉም የስሜት ህዋሳቶቼ በሚገባቸው ድምፅ ተንሾካሾከ።) ልታወሪልኝ የምትፈልጊው ነገር አለ? እ? እሺ እንዳድርልሽ ትፈልጊያለሽ?”
“አይይይ አልፈልግም።” አልኩት። አጠገቤ እንዲሆን እኮ እፈልጋለሁ። ሲነካኝ ግን እበረግጋለሁ። እጆቼን ሲያሻሽ ፣ ቅድም እንዳደረገው አንገቴ ስር ሲስመኝ ፣ ዓይኖቼን በሚለማመጡ ዓይኖቹ ሲያያቸው…… መሸሽ እፈልጋለሁ። እንዲህ ሲያደርግ የሚሰማኝን ስሜት ስለምጠላው አይደለም። ስለምወደው እንጂ። ነገር ግን ደስ የሚለኝ አዲስ ስሜት ያስፈራኛል። ሁሌም ቢሆን ያልተለማመድነው አዲስ ነገር፣ አዲስ ሀሳብ፣ አዲስ ስሜት……… ብቻ አዲስ ልምድ መጠኑ ቢለያይም ፍርሃት ያጅበዋል። ምክንያቱ ደግሞ ውጤቱ ከግምት ያለፈ ማረጋገጫ የለውም። ለዚህ ይመስለኛል የብዙ ሰዎች ኑሮ የተለመደ እና የተደጋገመ የሚሆነው። ከአዲስ ነገር ጋር አብሮ ብልጭ የሚለውን ፍርሃት መጋፈጥ የቻሉ ጥቂት ደፋሮች ለአለማችን አዳዲስ ሀሳቦች እና ፈጠራዎች አበርክተዋል።
“እሺ እኛ ቤት እንሂድ? ከካስዬ ጋር ስትጫወቺ ይለቅሻል። እንሂድ?”
“አይ… … ስለትዝታ የደረስኩበት ነገር አለኝ አላልክም ነበር? እሱን እንድትነግረኝ ነው።” የሚል ምክንያት ነበር የመጣልኝ
“ስለትዝታ ልትጠይቂኝ ነው እጅሽ የሚያልብሽ?( ያላበው መዳፌን በእጁ እየጠረገ ያደርቃል። ይሄኔ እኮ ድምፅ ከጆሮ ውጪ በሌላ የስሜት ህዋስ እንዴት ይተረጎማል? ብሎ የሚጠይቅ አላዋቂ አይጠፋም። አሁን ፍትህ እያወራ ያለበት ባለጣዕም ድምፅ ቀላል ይጣፍጣል?) ስለትዝታ ልትጠይቂኝ ነው ዓይንሽ የሚሸሸኝ? (ይሄን ያለበት ድምፅስ ቀላል የሚያውድ መዓዛ አለው?) ስለትዝታ ልትጠይቂኝ ነው ጉንጭሽ የቀላው? (ይሄኛው ቀለማት አሉት። ዓይን የሚይዝ የቀለም ስብጥር) ስለትዝታ ልትጠይቂኝ ነው ቃላት ለማውጣት ያማጥሽው?( ይሄኛው እንደሚያባብል የውሃ ዳር ንፋስ በቆዳዬ ላይ ሽውውውው እያለ ይዳብሰኛል።)” ጭራሽ የማወራው ጠፋብኝ። በዛው ድምፅ ቀጠለ
“ስለስራ ስታወሪ ዓይኖችሽ ዓይኖቼን ያሳድዳሉ ፣ አንገትሽን ቀና አድርገሽ የምትናገሪው ተፅፎ የተሰጠሽ አይነት ‘articulated’ ነው፣ በጥያቄሽ ብዛት እኔን ያልበኛል። …… ንገሪኝ ምን ልትዪኝ ነበር እጄን የያዝሽኝ?” (ይሄንን ድምፅ ጥፍሬ እና ፀጉሮቼ እንኳን ላይሰሙት አይችሉም።)
“ምንም!! ምንም የምልህ ነገር ኖሮኝ አይደለም። …… በቃ እንድትቆይ ብቻ ፈልጌ ነው።”
“እሺ (ያልከለለውን ፀጉሬን ወደኋላ እያደረገ) እሺ እንድቆይልሽ እስከምትፈልጊው ጊዜ ሙሉ የእድሜዬን ቁጥርም ቢሆን እቆይልሻለሁ። ምን እያደረግኩልሽ እንድቆይ ነው የምትፈልጊው?”
“አላውቅም!! ፍትህ የተሰማኝን ስለነገርኩህ እንዳፍር እያደረግከኝ ነው።” ስለው ፈገግ ማለቱን ሳላየው በምን አወቅኩ? ምራቄን እየደጋገምኩ በሚያስተጋባ ጉሮሮዬ የምውጠው ምን ሆኜ ነው? አፍንጫዬ ሳይቀር የሚያልበኝስ?
“እሺ!!” ብሎኝ እጄን ለቀቀኝ። ከሶፋው ላይ ትንሽዬዋን ትራስ አንስቶ እኔ ከተቀመጥኩበት በተቃራኒ ጥግ ተቀመጠ።ትራሷን ጭኑ ላይ ካስቀመጠ በኋላ በእጁ እየመታ ጠቆመኝ። ጀርባዬን ሰጥቼው እግሬን ሰቅዬ እሱን ተንተርሼ ተጋደምኩ።
“ፊትሽን አትከልዪኝ። ወደዚህ ዙሪና ከፈለግሽ ዓይንሽን ጨፍኚ።” አለኝ ቀጠለና። እንዳለኝ አደረግኩ። ዓይኔን ግን አልጨፈንኩም። ፀጉሬን በጣቱ እያበጠረ ለደቂቃዎች ካለምንም የቃላት ልውውጥ ከቆየን በኋላ።
“እንቅልፍሽ ከመጣ መተኛት ትችያለሽ።” አለኝ
“ከዛስ? አንተስ?”
“ያላደለው ጨለማ ላይ አፍጥጦ ያድር የለ? አንቺን የመሰለ ውበት ላይ አፍጥጦ ማደር ተገኝቶ ነው? ውብ’ኮ ነሽ ካስዬ ይሙት! (እጄን የማስቀምጥበት አጥቼ አቅበዘበዝኩት።) እፍረትሽ መጣ?” ብሎኝ ሳቅ ሲል በጨረፍታ አየሁት።
” አንዳንድ ነገር ሳጣራ ነበር። ምን ያህል እንደሚጠቅመኝ ባላውቅም አንዳንድ መረጃዎች ……”
“እስኪ ንገረኝ።”
“የሟች ታሪክ ትዝታ ካለችው የራቀ ነው። ሟች የሰውየው ፍቅረኛ አልነበረችም። ከዚያ ቀን በፊትም ተያይተው አያውቁም። የምትማርበት
👍9
ትምህርት ቤት ጓደኞቿ የሞተች ዕለት መጥቶ ከትምህርት ቤቷ ወሰዳት ያሉትን ሰው አገኘሁት።”
“እና?” ከተጋደምኩበት ቀና ብዬ ለመልሱ አቆበቆብኩ። ፈገግ አለ። ‘ስለስራ ሲሆንማ እንዲህ ነው የምትሆኚው’ የሚል ትዝብት ያለበት ዓይነት ፈገግታ።
“ወንጀሉን መሸፈኛ ስራው ትዳር ፈላጊ አገናኝ ነው። ዋነኛ ስራው ተማሪ ህፃናትና ወጣት ሴቶችን ለከተማችን ዋልጌ ሀብታም ሽማግሌዎች ማቅረብ ነው። ‘ሀብታም የሆነ ባል ፈልጋለሁ ስላለችኝ ነው ያገናኘኋት።’ ባይ ነው። ትዝታ ለመጀመሪያ ጊዜ እቤታቸው የመጣችን ሴት ‘ልጄን በጥፊ ስለመታቻት’ በሚል ቀሽም ምክንያት ትገድላታለች ብሎ ማመን ይከብዳል። ካልሆነስ ማንን እየተከላከለች ነው? ሰውየውን? እሱስ ቢሆን ከዚያን ቀን በፊት አይቷት የማያውቃትን ሴት ለመግደል ምን በቂ ምክንያት ይኖረዋል?”
“አንድ የሆነ ነገር ግን አለ። ልጅ አለሽ ወይ ብላ የጠየቀችኝ ቀን በደንብ አስተውለሃታል? አነጋገሯ ለልጇ ብላ እየከፈለች ያለችው መስዋዕትነት እንደሆነ ነገር ነው።”
“ሌላው ነገር… …ማንም የሚያውቀው ሰው ክፉ ስለማያወራለት አጎቷ አንድ ትኩረቴን የሳበ መረጃ ሰማሁ። የትዝታ ፍቅረኛ ፣ የልጇ አባት ትዝታ እርጉዝ በነበረችበት ወቅት እቤታቸው ድረስ መጥቶ አጎትየውን ደብድቦት ሄደ። ከዚያ ቀን በኋላ ልጁን አየሁት የሚል ሰው የለም። ትዝታም ምንም ልትነግረኝ ፈቃደኛ አይደለችም። አጎትየው በሁለቱ ግንኙነት ደስተኛ ካልነበረ ጥቃት ሊያደርስ የሚገባው እሱ ሆኖ የተገላቢጦሽ እንዴት ሆነ?”
“እሱን እያሰብኩ ነበር። ጎብዘኻል ግን ደስ ብሎኛል።” አልኩት ለጊዜውም ቢሆን ያ የሚያሽኮረምመኝ ፍትህ ተዘንግቶኝ ዓይን ዓይኑን እያየሁ።
“በልብሽ ደምቄ ለመፃፍ የሚያስከፍለኝ ጉብዝናን ከሆነ እተጋለሁዋ ምን አማራጭ አለኝ?” አለኝ እሽኩርምሚቴን በሚያመጣው ድምፁ። ተመልሼ እንደመጀመሪያው እላዩ ላይ ተጋደምኩ እና ዓይኔን ጨፈንኩ። ፀጉሬን በጣቶቹ እያበጠረ መነሻም ማረፊያም የሌለው ወሬ እያወራኝ ለምን ያህል ደቂቃ እንደቆየ አላውቅም። እንቅልፍ ወስዶኝ የነቃሁት ለሊት ዘጠኝ ሰዓት ነው። የሶፋውን መደገፊያ ተደግፎ በተቀመጠበት እንቅልፍ ወስዶታል። ጣቶቹ ከፀጉሬ መሃል አልወጡም። በሁለት የሶፋ ትራስ እግሬን ሸፍኖ ከብርድ ከልሎልኛል። ሆስፒታል ለማደር አስቦ ስለነበር የወጣው ቱታ ሱሪና ጃኬት ነበር የለበሰው። ጃኬቱን አውልቆት እጄን አልብሶኝ በ‘ፓክ አውት’ ነበር። ቀሰቀስኩት።
” ፍትህ ተነስ በስርዓቱ ተኛ አንገትህን ያምሃል። ተነስ እኔ መኝታ ቤት ተኛ። እኔ እማዬ ክፍል እተኛለሁ።” ይሄን የሚለው በምክንያትና በእውቀት ካላመንኩ የሚለው ጭንቅላቴ ነው። ልቤ ግን ከአጠገቡ መራቅን አልፈለገም።
“ከአንቺጋ እንድተኛ ካልፈቀድሽልኝ እዚሁ ሶፋ ላይ የምለብሰው ስጪኝና እተኛለሁ።” አለኝ አይኑን እንኳን አስተካክሎ ሳይገልጥ። ግራ ገባኝ ምን እንደምለው። ያንን እሱም ያወቀ መሰለኝ
“አብረን ተኝተን ነበር እኮ! አልጋ ላይ ሲሆን ምኑ ይለያል? ራሁ ስወድሽ አታወሳስቢው።”
“እሺ!” እያልኩት ወደመኝታዬ ገባሁ። ተከትሎኝ ገብቶ ጫማውን ብቻ አውልቆ ቀድሞኝ አልጋ ልብሶቹ ውስጥ ገብቶ በጀርባው ተኛ። አይኑን ጨፍኖ እጁን ለማቀፍ ዘረጋልኝ። አለማወሳሰብ ይሔ መሆኑን እየገመትኩ እቅፉ ውስጥ ገባሁ። በሁለቱም እጆቹ ደረቱ ላይ አጣብቆ አቅፎኝ ተኛ።… … አፌን እየሞላ እና ጉሮሮዬ ውስጥ የገደል ማሚቶ እየሰራ የሚያልፈውን ምራቄን እየዋጥኩ፤ ድው ድውታው ለእርሱ የሚሰማውን ልቤን ለመቆጣጠር እየታገልኩ የሚቀጥለውን እንቅስቃሴ ጠበቅኩ።… … ጠበቅኩ። …… ጠበቅኩ። …ተኝቷል። …… እንቅልፍ ወስዶታል። ካለፍርሃት ተኛሁ።
🌑ይቀጥላል➡️
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ Like Like👍
አስተያየት ካሎ በ @atronosebot አድርሱን
“እና?” ከተጋደምኩበት ቀና ብዬ ለመልሱ አቆበቆብኩ። ፈገግ አለ። ‘ስለስራ ሲሆንማ እንዲህ ነው የምትሆኚው’ የሚል ትዝብት ያለበት ዓይነት ፈገግታ።
“ወንጀሉን መሸፈኛ ስራው ትዳር ፈላጊ አገናኝ ነው። ዋነኛ ስራው ተማሪ ህፃናትና ወጣት ሴቶችን ለከተማችን ዋልጌ ሀብታም ሽማግሌዎች ማቅረብ ነው። ‘ሀብታም የሆነ ባል ፈልጋለሁ ስላለችኝ ነው ያገናኘኋት።’ ባይ ነው። ትዝታ ለመጀመሪያ ጊዜ እቤታቸው የመጣችን ሴት ‘ልጄን በጥፊ ስለመታቻት’ በሚል ቀሽም ምክንያት ትገድላታለች ብሎ ማመን ይከብዳል። ካልሆነስ ማንን እየተከላከለች ነው? ሰውየውን? እሱስ ቢሆን ከዚያን ቀን በፊት አይቷት የማያውቃትን ሴት ለመግደል ምን በቂ ምክንያት ይኖረዋል?”
“አንድ የሆነ ነገር ግን አለ። ልጅ አለሽ ወይ ብላ የጠየቀችኝ ቀን በደንብ አስተውለሃታል? አነጋገሯ ለልጇ ብላ እየከፈለች ያለችው መስዋዕትነት እንደሆነ ነገር ነው።”
“ሌላው ነገር… …ማንም የሚያውቀው ሰው ክፉ ስለማያወራለት አጎቷ አንድ ትኩረቴን የሳበ መረጃ ሰማሁ። የትዝታ ፍቅረኛ ፣ የልጇ አባት ትዝታ እርጉዝ በነበረችበት ወቅት እቤታቸው ድረስ መጥቶ አጎትየውን ደብድቦት ሄደ። ከዚያ ቀን በኋላ ልጁን አየሁት የሚል ሰው የለም። ትዝታም ምንም ልትነግረኝ ፈቃደኛ አይደለችም። አጎትየው በሁለቱ ግንኙነት ደስተኛ ካልነበረ ጥቃት ሊያደርስ የሚገባው እሱ ሆኖ የተገላቢጦሽ እንዴት ሆነ?”
“እሱን እያሰብኩ ነበር። ጎብዘኻል ግን ደስ ብሎኛል።” አልኩት ለጊዜውም ቢሆን ያ የሚያሽኮረምመኝ ፍትህ ተዘንግቶኝ ዓይን ዓይኑን እያየሁ።
“በልብሽ ደምቄ ለመፃፍ የሚያስከፍለኝ ጉብዝናን ከሆነ እተጋለሁዋ ምን አማራጭ አለኝ?” አለኝ እሽኩርምሚቴን በሚያመጣው ድምፁ። ተመልሼ እንደመጀመሪያው እላዩ ላይ ተጋደምኩ እና ዓይኔን ጨፈንኩ። ፀጉሬን በጣቶቹ እያበጠረ መነሻም ማረፊያም የሌለው ወሬ እያወራኝ ለምን ያህል ደቂቃ እንደቆየ አላውቅም። እንቅልፍ ወስዶኝ የነቃሁት ለሊት ዘጠኝ ሰዓት ነው። የሶፋውን መደገፊያ ተደግፎ በተቀመጠበት እንቅልፍ ወስዶታል። ጣቶቹ ከፀጉሬ መሃል አልወጡም። በሁለት የሶፋ ትራስ እግሬን ሸፍኖ ከብርድ ከልሎልኛል። ሆስፒታል ለማደር አስቦ ስለነበር የወጣው ቱታ ሱሪና ጃኬት ነበር የለበሰው። ጃኬቱን አውልቆት እጄን አልብሶኝ በ‘ፓክ አውት’ ነበር። ቀሰቀስኩት።
” ፍትህ ተነስ በስርዓቱ ተኛ አንገትህን ያምሃል። ተነስ እኔ መኝታ ቤት ተኛ። እኔ እማዬ ክፍል እተኛለሁ።” ይሄን የሚለው በምክንያትና በእውቀት ካላመንኩ የሚለው ጭንቅላቴ ነው። ልቤ ግን ከአጠገቡ መራቅን አልፈለገም።
“ከአንቺጋ እንድተኛ ካልፈቀድሽልኝ እዚሁ ሶፋ ላይ የምለብሰው ስጪኝና እተኛለሁ።” አለኝ አይኑን እንኳን አስተካክሎ ሳይገልጥ። ግራ ገባኝ ምን እንደምለው። ያንን እሱም ያወቀ መሰለኝ
“አብረን ተኝተን ነበር እኮ! አልጋ ላይ ሲሆን ምኑ ይለያል? ራሁ ስወድሽ አታወሳስቢው።”
“እሺ!” እያልኩት ወደመኝታዬ ገባሁ። ተከትሎኝ ገብቶ ጫማውን ብቻ አውልቆ ቀድሞኝ አልጋ ልብሶቹ ውስጥ ገብቶ በጀርባው ተኛ። አይኑን ጨፍኖ እጁን ለማቀፍ ዘረጋልኝ። አለማወሳሰብ ይሔ መሆኑን እየገመትኩ እቅፉ ውስጥ ገባሁ። በሁለቱም እጆቹ ደረቱ ላይ አጣብቆ አቅፎኝ ተኛ።… … አፌን እየሞላ እና ጉሮሮዬ ውስጥ የገደል ማሚቶ እየሰራ የሚያልፈውን ምራቄን እየዋጥኩ፤ ድው ድውታው ለእርሱ የሚሰማውን ልቤን ለመቆጣጠር እየታገልኩ የሚቀጥለውን እንቅስቃሴ ጠበቅኩ።… … ጠበቅኩ። …… ጠበቅኩ። …ተኝቷል። …… እንቅልፍ ወስዶታል። ካለፍርሃት ተኛሁ።
🌑ይቀጥላል➡️
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ Like Like👍
አስተያየት ካሎ በ @atronosebot አድርሱን
👍8
#ራሴው_ማበዴ_ነው
:
#ክፍል_ዘጠኝ
:
✍ደራሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
:
...“አገኘሁት! ራሁ አገኘሁት!” ይለኛል የሆስፒታሉ ኮሪደር መሃል እየደነሰ
“ምኑን? እስኪ አንዴ ዳንስህን አቁመህ ንገረኝ!”
“የትዝታን ፍቅረኛ አገኘሁት!”
“በጣም ጥሩ! የሚጠቅም መረጃ አገኘህ?”
“ገና ነው። ደቡብ አፍሪካ ነው ያለው። ከሀገር እንዲወጣ ያደረገው ማን እንደሆን ገምቺ? የትዝታ አጎት! አስፈራርተውት ነው ከሀገር እንዲወጣ ያደረጉት።”
“ለምን?”
“ትዝታን ለሌላ ለተከበረ ሰው ሊድሯት እንደሆነና ከሷ ህይወት እንዲወጣ እንዳስፈራሩት ጓደኛው ነው መረጃ የሰጠኝ። የሚደውልለትን ስልክ ሰጥቶኝ ደውዬለት ነበር።”
“እና?”
” በዚህ ርቀት ሆኖ እንኳን ይፈራቸዋል። ገና ስለትዝታ ሳነሳበት ‘ሰውየው አረመኔ ነው። አታውቁትም። ትንፍሽ ብል ይገድለኛል።’ አለኝ። ትዝታ ያለችበትን ሁኔታ አስረዳሁት። ልጁ ያለእናትና አባት መቅረቷ መሆኑን ስነግረው ስራ ቦታ መሆኑን እና መልሶ እንደሚደውልልኝ ነግሮኝ ስልኩን ዘጋው።”
“በቃ?”
“ለጊዜው አዎን በቃ!”
“እና የሚያስደንስህ ይሄ ነው? ገና የመፅሃፉን ሽፋን እየገለጥክ እንደሆነ አልገባህም ልበል? ገና ገፅ አንድን እንኳን አላነበብክም እኮ!”
“ራሁዬ ገፅ አንድ ላይ ነኝ ማለት ታዲያ ቢያንስ ትክክለኛውን ትራክ አጊንቻለሁ ማለት አይደል? የተሳሳተ መፅሃፍ ካልገለጥኩ am good ማለት ነው። ሌላው የውልሽ ትዝታን አናገርኳት። ‘ተወኝ’ ከሚል ቃል ውጪ ትንፍሽ ብላ የማታውቅ ልጅ። የልጇን አባት እንዳገኘሁት ስነግራት ከመቀመጫዋ ዘላ ተነስታ ‘በህይወት አለ?’ ብላ ነበር የጠየቀችኝ። ደስ ያላት ትመስላለች። ሞቷል ብላ አስባ ነበር ማለት ነው። ከዚህ ተጨማሪ ነገር ልትናገር አልፈለገችም። ይልቅ ያሰብሽውን ንገሪኝ።”
“የማስበውማ እንዴትም ብለህ ድጋሚ ልታናግረው ይገባል! ስለሰውየው የሚያውቀው ነገር የሚያስገድለው ወይም ከሀገር የሚያሰድደው ከሆነ ሰውየው እንዴት ያለ ወንጀል ውስጥ የዘቀጠ ቢሆን ነው? ስለሰውየው ተጨማሪ መረጃዎች መሰብሰብ አለብህ። የማስበው ዜሮ ላይ እንዳለን ነው።”
በእርግጥ ለእርሱ ይሄን ልበለው እንጂ በትዝታ ጉዳይ የሚገኙት መረጃዎች ብጥቅጣቂና ለማስረጃነት የማይበቁ ምስክርነቶች መሆናቸው ተስፋ አስቆራጭ ሆኖ እንኳን በየቀኑ መረጃ ለማግኘት የሚያደርገው ጥረት እያስገረመኝ ነው። ካሳሁን በሁኔታው መደሰቱን እያመሰገነኝ ነግሮኛል።
“እሺ እማዬን ተሰናብቻት ልውጣ!” ብሎኝ አልፎኝ ወደ ውስጥ ገባ። እማዬ ዛሬ ጠዋት እንዲህ ብላኝ ነበር።
“ሚሚሾ ወጣትነትሽን ለእኔ ብለሽ ገብረሻል። ለራስሽ መኖር ያለብሽ ጊዜ የደረሰ ይመስለኛል። ፍትህ መልካም ሰው ነው። ይወድሻል። አትግፊው።”
“በምን አወቅሽ?” ስላት ሳቀችብኝ። …… ፍትህን እንደወደደችው አውቃለሁ። ከእርሱም ጋር ሆነ ከካሳሁን ጋር ስትጫወት ያለስስት ነው። እነሱ አጠገቧ ሲኖሩ ደስተኛ ናት።…… ካሳሁን ሲኖር ፍትህን ያበሽቀዋል። እኔና እማዬ እንስቅበታለን። እሱ ሳይኖር እማዬና ፍትህ በእኔ ሙድ እየያዙ ይስቃሉ። …… ሆስፒታል ያለን አይመስልም… …… ወደሞት እየተንደረደረች ያለች እማዬን የከበብን አንመስልም። አዲስ ህፃን ወደቤተሰቡ የቀላቀለች እናት ከበን የምንደሰት ነው የምንመስለው። አባቴም በየቀኑ መምጣቱን አላቆመም። እሱ ሲመጣ እኔ እወጣለሁ። ላናግረው እንደማልፈልግ እርሱም ያውቃል። አይሞክርም። ከእኔ ይልቅ ከፍትህ ጋር ያወራሉ። እንዲህ እየሆነ እማዬ ሆስፒታል ከገባች አንድ ወር አልፏታል።
” ፍቅር ብርሃን ነው ሚሚሾ አይደበቅም። በምንም ልትከልዪው ብትሞክሪ የብርሃን ፍንጣቂዎቹ ቀዳዳ እየፈለጉ ያበራሉ። እንደሚወድሽ ትጠራጠሪያለሽ?” አለችኝ።
“አላውቅም እማ! ገና አጭር ጊዜ ነው ካወቅኩት እንኳን። አላውቀውም!” ከማለት ውጪ ግራ ስለሚያጋባኝ ድርጊቱ ለሷ ማውራት አልችልም። አንዴ በፍቅር አክናፍ አፈናጦኝ አርያም የደረስኩ እንዲሰማኝ ያደርገኝና መልሶ ለቀናት በመሃከላችን ከጓደኝነት የዘለለ ነገር እንደሌለ ያስመስላል። ባለፈው ለት አቅፎኝ አድሮ ጠዋት ስነቃ አጠገቤ ካለመኖሩ በላይ ሳገኘው ማታ እቅፉ ውስጥ እንዳልነበርኩ ያስመስላል። አላውቅም! እንዴትስ ማወቅ እችላለሁ? አዝኖልኝ ይሆን ወዶኝ ራሱ ካልነገረኝ በምን አውቃለሁ?
“ሚሚሾዬ የምትፈልጊውን ነገር ለማግኘት ምቹ ጊዜ እስኪመጣ ወይም ጊዜው የምትፈልጊውን ይዞ እስኪመጣ ቁጭ ብለሽ ለመጠበቅ ህይወት በጣም አጭር ናት። በእጅሽ ያለውን ጊዜ ምቹ አድርጊው።” አለችኝ የተዘጋጀ ምግብ እንደመጉረስ ቀላል ነገር የተናገረች ይመስል ልዝብ ብላ።
በቆምኩበት ሀሳብ ሳመነዥክ ፍትህ ተመልሶ መጣ።
“ባለፈው እማዬ ራሷን የጎዳች ቀን ስናወራ የእህቴን ሰርግ ላለመሄድ እና ለአባቴ ጥብቅና ላለመቆም በምላሹ አንድ ነገር እንዳደርግልህ ጠይቀኸኝ ነበር። ታስታውሳለህ? ምን ነበር?” አልኩት ለመሄድ እየተጣደፈ ስለነበረ ላቆየው ፈልግያለሁ።
“እኔ እንጃ! ብዬሽ ነበር? ትዝ አይለኝም።” አለኝ ጥድፈቱን ሳያቆም ትከሻዬን ጨበጥ አድርጎኝ በቆምኩበት ትቶኝ ሄደ። ከፋኝ። የሚናገረውንና የሚያደርገውን ነገር በፍቅር የምተረጉመው ብቻዬን እንደሆነ ተሰማኝ።ለእርሱ ከቀን ተቀን የተለመደ ድርጊትና ንግግር በላይ ዋጋ ያለው ነገር አልነበረም ማለት ነው። እግሬን እየጎተትኩ እማዬጋ ተመለስኩ። እማዬ እየደጋገመች ምን እንደሆንኩ ትጠይቀኛለች። እየደጋገምኩ የሆንኩት ያለመኖሩን እመልስላታለሁ። ሲመሻሽ ካሳሁን ቢመጣም እንደሌላው ቀን መደሰት አልቻልኩም። አንድ የሰውነቴ አካል የከዳኝ መሰለኝ። በሩ በተከፈተ ቁጥር እሱ እየመሰለኝ አፈጣለሁ። አባቴ ሊያድር ስለመጣ እኔና ካሳሁን ወደየቤታችን ሄድን። ጭራሽ ያለወትሮው ስልክም ሳይደውልልኝ አደረ። በሚቀጥለው ቀን ምሽት ሆስፒታል እማዬጋ ቁጭ ብዬ ደውሎልኝ ሊያገኘኝ እንደሚፈልግ ነገረኝ።
“ታዲዎስ ተገድሏል!” አለኝ የተቀጣጠርንበት ካፌ ደርሼ ገና ሳልቀመጥ። ያለኝ ገብቶኝ ሳያልቅ ቀጠለ “ያልታወቁ ሰዎች በጩቤ ወግተውት መንገድ ላይ ወድቆ ነው የተገኘው።” ተስፋ የቆረጠ፣ የተናደደ፣ ያዘነ… ብዙ ዓይነት ስሜት ነው የሚፈራረቅበት። “…… ጓደኛው ነው ደውሎ የነገረኝ። ምን እንዳለኝ ታውቂያለሽ? ‘በሰላም ይኖር የነበረውን ልጅ አስገደልከው። አንተ ነህ ያስገደልከው።’ አለኝ።” የተፈጠረው ነገር በጣም ስሜታዊ ስላደረገው ቅደም ተከተሉን ያልጠበቀ ወሬ ነው የሚያወራኝ።
የትዝታ ፍቅረኛ ታዲዎስ ባልታወቁ ሰዎች ተገድሎ ለቤተሰቡ መርዶ ተረድቷቸው አስክሬን እየጠበቁ ነው። ፍትህ በተደጋጋሚ ደውሎለት ስልኩ እንቢ ብሎት ነበር። የትዝታ አባት ትንፍሽ ቢል እንደሚገድለው ለፍትህ በተናገረ ማግስት ሞቶ መገኘቱ አጋጣሚ ሊሆን አይችልም። ግን ማስረጃ የለም። አጋጣሚ ግጥምጥሞሽም ሊሆን ይችላል። የሟች ጓደኛ ሞቱ ከፍትህ ጋር ከማውራቱ ጋር የተያያዘ መሆኑን በምን እርግጠኛ ሊሆን ቻለ?
“ትዝታ አንቺን ማግኘት ትፈልጋለች።” አለኝ በጎርናና ድምፅ “ምናልባት የምትነግርሽ ነገር ሳይኖር አይቀርም። የታዲዎስን አሟሟት ስነግራት ኩርምት ብላ ነበር የተንሰቀሰቀችው። እሷም ‘አስገደልከው’ አለችኝ። ማን? ለምን? ለሚለው ጥያቄዬ ግን መልሷ ዝምታ ነበር።” ሀዘናቸው ተጋብቶበታል። እሱም አስክሬን የሚጠብቅ ለቀስተኛ መስሏል።
“እሺ! አንተ ተረጋጋ እና ወዴት እንደሚወስደን እናስብ።”
“አይታይሽም? ወዴትም መሄጃ የለም።”
“ገና ከአሁኑ ተስፋ ቆርጫለሁ እንዳትለኝ? ገና ሳትጀምረው ይሄ ጉዳይ የተወሳሰበ ሊሆን እንደሚችል ነግሬህ ነበር። ገና ከመጀመርህ እጅ መስጠትህ ነው?” ስለው በቃል አልመለሰልኝም። ሁኔታው ግን
:
#ክፍል_ዘጠኝ
:
✍ደራሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
:
...“አገኘሁት! ራሁ አገኘሁት!” ይለኛል የሆስፒታሉ ኮሪደር መሃል እየደነሰ
“ምኑን? እስኪ አንዴ ዳንስህን አቁመህ ንገረኝ!”
“የትዝታን ፍቅረኛ አገኘሁት!”
“በጣም ጥሩ! የሚጠቅም መረጃ አገኘህ?”
“ገና ነው። ደቡብ አፍሪካ ነው ያለው። ከሀገር እንዲወጣ ያደረገው ማን እንደሆን ገምቺ? የትዝታ አጎት! አስፈራርተውት ነው ከሀገር እንዲወጣ ያደረጉት።”
“ለምን?”
“ትዝታን ለሌላ ለተከበረ ሰው ሊድሯት እንደሆነና ከሷ ህይወት እንዲወጣ እንዳስፈራሩት ጓደኛው ነው መረጃ የሰጠኝ። የሚደውልለትን ስልክ ሰጥቶኝ ደውዬለት ነበር።”
“እና?”
” በዚህ ርቀት ሆኖ እንኳን ይፈራቸዋል። ገና ስለትዝታ ሳነሳበት ‘ሰውየው አረመኔ ነው። አታውቁትም። ትንፍሽ ብል ይገድለኛል።’ አለኝ። ትዝታ ያለችበትን ሁኔታ አስረዳሁት። ልጁ ያለእናትና አባት መቅረቷ መሆኑን ስነግረው ስራ ቦታ መሆኑን እና መልሶ እንደሚደውልልኝ ነግሮኝ ስልኩን ዘጋው።”
“በቃ?”
“ለጊዜው አዎን በቃ!”
“እና የሚያስደንስህ ይሄ ነው? ገና የመፅሃፉን ሽፋን እየገለጥክ እንደሆነ አልገባህም ልበል? ገና ገፅ አንድን እንኳን አላነበብክም እኮ!”
“ራሁዬ ገፅ አንድ ላይ ነኝ ማለት ታዲያ ቢያንስ ትክክለኛውን ትራክ አጊንቻለሁ ማለት አይደል? የተሳሳተ መፅሃፍ ካልገለጥኩ am good ማለት ነው። ሌላው የውልሽ ትዝታን አናገርኳት። ‘ተወኝ’ ከሚል ቃል ውጪ ትንፍሽ ብላ የማታውቅ ልጅ። የልጇን አባት እንዳገኘሁት ስነግራት ከመቀመጫዋ ዘላ ተነስታ ‘በህይወት አለ?’ ብላ ነበር የጠየቀችኝ። ደስ ያላት ትመስላለች። ሞቷል ብላ አስባ ነበር ማለት ነው። ከዚህ ተጨማሪ ነገር ልትናገር አልፈለገችም። ይልቅ ያሰብሽውን ንገሪኝ።”
“የማስበውማ እንዴትም ብለህ ድጋሚ ልታናግረው ይገባል! ስለሰውየው የሚያውቀው ነገር የሚያስገድለው ወይም ከሀገር የሚያሰድደው ከሆነ ሰውየው እንዴት ያለ ወንጀል ውስጥ የዘቀጠ ቢሆን ነው? ስለሰውየው ተጨማሪ መረጃዎች መሰብሰብ አለብህ። የማስበው ዜሮ ላይ እንዳለን ነው።”
በእርግጥ ለእርሱ ይሄን ልበለው እንጂ በትዝታ ጉዳይ የሚገኙት መረጃዎች ብጥቅጣቂና ለማስረጃነት የማይበቁ ምስክርነቶች መሆናቸው ተስፋ አስቆራጭ ሆኖ እንኳን በየቀኑ መረጃ ለማግኘት የሚያደርገው ጥረት እያስገረመኝ ነው። ካሳሁን በሁኔታው መደሰቱን እያመሰገነኝ ነግሮኛል።
“እሺ እማዬን ተሰናብቻት ልውጣ!” ብሎኝ አልፎኝ ወደ ውስጥ ገባ። እማዬ ዛሬ ጠዋት እንዲህ ብላኝ ነበር።
“ሚሚሾ ወጣትነትሽን ለእኔ ብለሽ ገብረሻል። ለራስሽ መኖር ያለብሽ ጊዜ የደረሰ ይመስለኛል። ፍትህ መልካም ሰው ነው። ይወድሻል። አትግፊው።”
“በምን አወቅሽ?” ስላት ሳቀችብኝ። …… ፍትህን እንደወደደችው አውቃለሁ። ከእርሱም ጋር ሆነ ከካሳሁን ጋር ስትጫወት ያለስስት ነው። እነሱ አጠገቧ ሲኖሩ ደስተኛ ናት።…… ካሳሁን ሲኖር ፍትህን ያበሽቀዋል። እኔና እማዬ እንስቅበታለን። እሱ ሳይኖር እማዬና ፍትህ በእኔ ሙድ እየያዙ ይስቃሉ። …… ሆስፒታል ያለን አይመስልም… …… ወደሞት እየተንደረደረች ያለች እማዬን የከበብን አንመስልም። አዲስ ህፃን ወደቤተሰቡ የቀላቀለች እናት ከበን የምንደሰት ነው የምንመስለው። አባቴም በየቀኑ መምጣቱን አላቆመም። እሱ ሲመጣ እኔ እወጣለሁ። ላናግረው እንደማልፈልግ እርሱም ያውቃል። አይሞክርም። ከእኔ ይልቅ ከፍትህ ጋር ያወራሉ። እንዲህ እየሆነ እማዬ ሆስፒታል ከገባች አንድ ወር አልፏታል።
” ፍቅር ብርሃን ነው ሚሚሾ አይደበቅም። በምንም ልትከልዪው ብትሞክሪ የብርሃን ፍንጣቂዎቹ ቀዳዳ እየፈለጉ ያበራሉ። እንደሚወድሽ ትጠራጠሪያለሽ?” አለችኝ።
“አላውቅም እማ! ገና አጭር ጊዜ ነው ካወቅኩት እንኳን። አላውቀውም!” ከማለት ውጪ ግራ ስለሚያጋባኝ ድርጊቱ ለሷ ማውራት አልችልም። አንዴ በፍቅር አክናፍ አፈናጦኝ አርያም የደረስኩ እንዲሰማኝ ያደርገኝና መልሶ ለቀናት በመሃከላችን ከጓደኝነት የዘለለ ነገር እንደሌለ ያስመስላል። ባለፈው ለት አቅፎኝ አድሮ ጠዋት ስነቃ አጠገቤ ካለመኖሩ በላይ ሳገኘው ማታ እቅፉ ውስጥ እንዳልነበርኩ ያስመስላል። አላውቅም! እንዴትስ ማወቅ እችላለሁ? አዝኖልኝ ይሆን ወዶኝ ራሱ ካልነገረኝ በምን አውቃለሁ?
“ሚሚሾዬ የምትፈልጊውን ነገር ለማግኘት ምቹ ጊዜ እስኪመጣ ወይም ጊዜው የምትፈልጊውን ይዞ እስኪመጣ ቁጭ ብለሽ ለመጠበቅ ህይወት በጣም አጭር ናት። በእጅሽ ያለውን ጊዜ ምቹ አድርጊው።” አለችኝ የተዘጋጀ ምግብ እንደመጉረስ ቀላል ነገር የተናገረች ይመስል ልዝብ ብላ።
በቆምኩበት ሀሳብ ሳመነዥክ ፍትህ ተመልሶ መጣ።
“ባለፈው እማዬ ራሷን የጎዳች ቀን ስናወራ የእህቴን ሰርግ ላለመሄድ እና ለአባቴ ጥብቅና ላለመቆም በምላሹ አንድ ነገር እንዳደርግልህ ጠይቀኸኝ ነበር። ታስታውሳለህ? ምን ነበር?” አልኩት ለመሄድ እየተጣደፈ ስለነበረ ላቆየው ፈልግያለሁ።
“እኔ እንጃ! ብዬሽ ነበር? ትዝ አይለኝም።” አለኝ ጥድፈቱን ሳያቆም ትከሻዬን ጨበጥ አድርጎኝ በቆምኩበት ትቶኝ ሄደ። ከፋኝ። የሚናገረውንና የሚያደርገውን ነገር በፍቅር የምተረጉመው ብቻዬን እንደሆነ ተሰማኝ።ለእርሱ ከቀን ተቀን የተለመደ ድርጊትና ንግግር በላይ ዋጋ ያለው ነገር አልነበረም ማለት ነው። እግሬን እየጎተትኩ እማዬጋ ተመለስኩ። እማዬ እየደጋገመች ምን እንደሆንኩ ትጠይቀኛለች። እየደጋገምኩ የሆንኩት ያለመኖሩን እመልስላታለሁ። ሲመሻሽ ካሳሁን ቢመጣም እንደሌላው ቀን መደሰት አልቻልኩም። አንድ የሰውነቴ አካል የከዳኝ መሰለኝ። በሩ በተከፈተ ቁጥር እሱ እየመሰለኝ አፈጣለሁ። አባቴ ሊያድር ስለመጣ እኔና ካሳሁን ወደየቤታችን ሄድን። ጭራሽ ያለወትሮው ስልክም ሳይደውልልኝ አደረ። በሚቀጥለው ቀን ምሽት ሆስፒታል እማዬጋ ቁጭ ብዬ ደውሎልኝ ሊያገኘኝ እንደሚፈልግ ነገረኝ።
“ታዲዎስ ተገድሏል!” አለኝ የተቀጣጠርንበት ካፌ ደርሼ ገና ሳልቀመጥ። ያለኝ ገብቶኝ ሳያልቅ ቀጠለ “ያልታወቁ ሰዎች በጩቤ ወግተውት መንገድ ላይ ወድቆ ነው የተገኘው።” ተስፋ የቆረጠ፣ የተናደደ፣ ያዘነ… ብዙ ዓይነት ስሜት ነው የሚፈራረቅበት። “…… ጓደኛው ነው ደውሎ የነገረኝ። ምን እንዳለኝ ታውቂያለሽ? ‘በሰላም ይኖር የነበረውን ልጅ አስገደልከው። አንተ ነህ ያስገደልከው።’ አለኝ።” የተፈጠረው ነገር በጣም ስሜታዊ ስላደረገው ቅደም ተከተሉን ያልጠበቀ ወሬ ነው የሚያወራኝ።
የትዝታ ፍቅረኛ ታዲዎስ ባልታወቁ ሰዎች ተገድሎ ለቤተሰቡ መርዶ ተረድቷቸው አስክሬን እየጠበቁ ነው። ፍትህ በተደጋጋሚ ደውሎለት ስልኩ እንቢ ብሎት ነበር። የትዝታ አባት ትንፍሽ ቢል እንደሚገድለው ለፍትህ በተናገረ ማግስት ሞቶ መገኘቱ አጋጣሚ ሊሆን አይችልም። ግን ማስረጃ የለም። አጋጣሚ ግጥምጥሞሽም ሊሆን ይችላል። የሟች ጓደኛ ሞቱ ከፍትህ ጋር ከማውራቱ ጋር የተያያዘ መሆኑን በምን እርግጠኛ ሊሆን ቻለ?
“ትዝታ አንቺን ማግኘት ትፈልጋለች።” አለኝ በጎርናና ድምፅ “ምናልባት የምትነግርሽ ነገር ሳይኖር አይቀርም። የታዲዎስን አሟሟት ስነግራት ኩርምት ብላ ነበር የተንሰቀሰቀችው። እሷም ‘አስገደልከው’ አለችኝ። ማን? ለምን? ለሚለው ጥያቄዬ ግን መልሷ ዝምታ ነበር።” ሀዘናቸው ተጋብቶበታል። እሱም አስክሬን የሚጠብቅ ለቀስተኛ መስሏል።
“እሺ! አንተ ተረጋጋ እና ወዴት እንደሚወስደን እናስብ።”
“አይታይሽም? ወዴትም መሄጃ የለም።”
“ገና ከአሁኑ ተስፋ ቆርጫለሁ እንዳትለኝ? ገና ሳትጀምረው ይሄ ጉዳይ የተወሳሰበ ሊሆን እንደሚችል ነግሬህ ነበር። ገና ከመጀመርህ እጅ መስጠትህ ነው?” ስለው በቃል አልመለሰልኝም። ሁኔታው ግን
👍8
የመሸነፍ ነው። ላፅናናው አልሞከርኩም። ምን እያሰበ እንደሆነ አላውቅም። እኔም በሀሳብ ተጠምጃለሁ። …… ሆስፒታል ማደር የእርሱ ተራ ነበረ።
“ወደቤት ሄደህ እረፍ! እማዬጋ እኔ እሆናለሁ።” አልኩት። ሄደ። እስከ ሶስት ቀን አልተመለሰም። ስልኩም ዝግ ነበር።
“ምን ሆኖ ነው? አስቀየምሽው እንዴ? ንገሪኝ ምን ተፈጥሮ ነው?” እማዬ ሶስት ቀን ስላላያት በጥያቄ ልትደፋኝ ነው። በስራ ምክንያት መሆኑን ብነግራትም አላመነችኝም። ካሳሁን ሲመጣም ተመሳሳይ መልስ ቢሰጣትም አላመነችም። አባቴ እንኳን ‘ምነው ጠፋ?’ ብሎ ጠየቀኝ።
ትዝታን ላገኛት ቀጠሮ አስይዤ አገኘኋት። አልቅሳ የሷን ጉዳይ እንድንተወው ለመነችኝ።
“ነገር መቆፈራችሁን ካልተዋችሁ ሌላ ተጨማሪ ሰው ይጎዳል።” አለችኝ ቃል በቃል።
“ተጨማሪ ማለት ከታዲዎስ ሌላ ማለትሽ ነው? ማነው የሚጎዳው? ልጅሽ? አጎትሽ? ሌላ ማን?” ከዚህ በኋላ ለጠየቅኳት ብዙ ጥያቄ መልስ አልሰጠችኝም።
“የልጅሽ አባት በሰው ነው የተገደለው። በእርግጠኝነት የምታውቂው ነገር አለ። መናገር ግን አትፈልጊም። ማንን ነው እየተከላከልሽ ያለሽው? ለልጅሽ ስታድግ ምን ምላሽ ይኖርሻል? አባቴስ ስትልሽ ምንድነው የምትያት? የአባቷን ገዳይ በነፃነት እንዲኖር የፈቀድሽበትን ምክንያት ታስረጃታለሽ? አባቷን በግፍ ላጣች ልጅ በቂ ምክንያትስ ይመስልሻል? ወይስ የአባቷን አሟሟት ትዋሻታለሽ? እስከመቼ? እውነት ቢረፍድም አንድ ቀን መውጣቷኮ አይቀርም።……… ” ምንም ቢሆን እናት ናትና ደካማ ጎኗ ልጇ ናት። ትዝታ ግን አልተሸነፈችም። ልወጣ ቦርሳዬን ሳነሳ
“የሱ ልጅ አይደለችም። አባቷ አይደለም።” አለችኝ። ከዛ በላይ ግን ልትነግረኝ አልፈለገችም። እየወጣሁ ለፍትህ ደወልኩለት እና ተገናኘን። ከትዝታ ጋር ያወራሁትን ነገርኩት። ሞቶ የነበረው መነቃቃቱ አንሰራርቶ መላምቶቹን ይነግረኝ ጀመር።
“የልጇ አባት እሱ ያለመሆኑን የተናገረችው እውነት ከሆነ ትዝታ ከሌላ ሰው ጋር ግንኙነት ነበራት። ምናልባትም አጎቷ ልድራት ነው ካለው ሰውጋ… … አንዱ ባለስልጣን ወይም አንዱ ሀብታም ይሆናል። ምናልባት ሟች በሆነ መንገድ ከዚህ ሰው ጋር ተያያዥነት ሊኖራት ይችላል። …… ምናልባት…… በስመአብ ወ ወልድ… … እኔ ያሰብኩትን አስበሃል?”
“በትክክል!!…… እያሰብኩ ያለሁት እንደሱ ነው!” አለኝ
🌑ይቀጥላል➡️
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ የኔ ምርጦች ቶሎ ቶሎ እንዲደርሶ በ Like Like እያጀረጉ
አስተያየት ካሎ በ @atronosebot አድርሱን
“ወደቤት ሄደህ እረፍ! እማዬጋ እኔ እሆናለሁ።” አልኩት። ሄደ። እስከ ሶስት ቀን አልተመለሰም። ስልኩም ዝግ ነበር።
“ምን ሆኖ ነው? አስቀየምሽው እንዴ? ንገሪኝ ምን ተፈጥሮ ነው?” እማዬ ሶስት ቀን ስላላያት በጥያቄ ልትደፋኝ ነው። በስራ ምክንያት መሆኑን ብነግራትም አላመነችኝም። ካሳሁን ሲመጣም ተመሳሳይ መልስ ቢሰጣትም አላመነችም። አባቴ እንኳን ‘ምነው ጠፋ?’ ብሎ ጠየቀኝ።
ትዝታን ላገኛት ቀጠሮ አስይዤ አገኘኋት። አልቅሳ የሷን ጉዳይ እንድንተወው ለመነችኝ።
“ነገር መቆፈራችሁን ካልተዋችሁ ሌላ ተጨማሪ ሰው ይጎዳል።” አለችኝ ቃል በቃል።
“ተጨማሪ ማለት ከታዲዎስ ሌላ ማለትሽ ነው? ማነው የሚጎዳው? ልጅሽ? አጎትሽ? ሌላ ማን?” ከዚህ በኋላ ለጠየቅኳት ብዙ ጥያቄ መልስ አልሰጠችኝም።
“የልጅሽ አባት በሰው ነው የተገደለው። በእርግጠኝነት የምታውቂው ነገር አለ። መናገር ግን አትፈልጊም። ማንን ነው እየተከላከልሽ ያለሽው? ለልጅሽ ስታድግ ምን ምላሽ ይኖርሻል? አባቴስ ስትልሽ ምንድነው የምትያት? የአባቷን ገዳይ በነፃነት እንዲኖር የፈቀድሽበትን ምክንያት ታስረጃታለሽ? አባቷን በግፍ ላጣች ልጅ በቂ ምክንያትስ ይመስልሻል? ወይስ የአባቷን አሟሟት ትዋሻታለሽ? እስከመቼ? እውነት ቢረፍድም አንድ ቀን መውጣቷኮ አይቀርም።……… ” ምንም ቢሆን እናት ናትና ደካማ ጎኗ ልጇ ናት። ትዝታ ግን አልተሸነፈችም። ልወጣ ቦርሳዬን ሳነሳ
“የሱ ልጅ አይደለችም። አባቷ አይደለም።” አለችኝ። ከዛ በላይ ግን ልትነግረኝ አልፈለገችም። እየወጣሁ ለፍትህ ደወልኩለት እና ተገናኘን። ከትዝታ ጋር ያወራሁትን ነገርኩት። ሞቶ የነበረው መነቃቃቱ አንሰራርቶ መላምቶቹን ይነግረኝ ጀመር።
“የልጇ አባት እሱ ያለመሆኑን የተናገረችው እውነት ከሆነ ትዝታ ከሌላ ሰው ጋር ግንኙነት ነበራት። ምናልባትም አጎቷ ልድራት ነው ካለው ሰውጋ… … አንዱ ባለስልጣን ወይም አንዱ ሀብታም ይሆናል። ምናልባት ሟች በሆነ መንገድ ከዚህ ሰው ጋር ተያያዥነት ሊኖራት ይችላል። …… ምናልባት…… በስመአብ ወ ወልድ… … እኔ ያሰብኩትን አስበሃል?”
“በትክክል!!…… እያሰብኩ ያለሁት እንደሱ ነው!” አለኝ
🌑ይቀጥላል➡️
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ የኔ ምርጦች ቶሎ ቶሎ እንዲደርሶ በ Like Like እያጀረጉ
አስተያየት ካሎ በ @atronosebot አድርሱን
👍3
#ራሴው_ማበዴ_ነው
:
#ክፍል_አስር
:
✍ደራሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
:
...የገዛ ሚስትህ በአደባባይ አብረሃት እየሄድክ ጡቶቿን የከለላቸውን ጨርቆች ገፋ ሳምልኝ ብትልህ ብልግና ይሆንብሃል። በሷ ድርጊት አንተ ትሸማቀቃለህ። መኝታ ቤታችሁ ውስጥ ራቁቷን ሆና ያንኑ ነገር ብትልህ ለቦታው የሚገባ ቅድስና አድርገህ ልትቆጥረው ትችላለህ። ምናልባትም ከዛ በላይ ‘ስድ’ ብትሆንልህ ያምርሃል።
በመንፈሳዊው ዓለም የመጀመሪያው ለሰው ልጆች የተሰጠ የተፃፈ ህግ አስርቱ ትዕዛዛት ናቸው። አትግደል የሚል ህግ ፅፎ ሰጥቷቸዋል። ጠላት በተነሳባቸው ጊዜ ግን አሳልፌ ሰጥቻችኋለሁና ዝመቱባቸው ብሎ እልፎች ያስገድላል።
በምድረኛው ህግም መግደል ወንጀል ነው ይልሃል። አንዳንድ ወንጀሎች ግን በዛው ህግ በሞት ያስቀጣሉ። እናም ፍትህ ነው ይልሃል። በተመሳሳይ በቀል ሀጢያት ነው ይሉሃል። የበደለህን ሰው አስጠፍንገህ ወህኒ ማስወርወር ግን በቀል ሳይሆን ፍትህ ነው ትባላለህ። ምናልባት አንተም ከዛ በላይ የምታደርገው ላይኖር ይችል ይሆናል እኮ!
አየህ በዚህኛው አለም ስትኖር ሀጢያት ወይ ፅድቅ፣ ልክ ወይ ስህተት፣ መልካም ወይም ክፉ፣ ብልግና ወይ ጨዋነት… እነዚህ አንዱ ከሌላኛው ተቃራኒ ዋልታ የሚገኝ መቼም የማይስማሙ ሊመስል ይችላል። አይደለም! እንደውም አንዱ በአንደኛው የሚተካካበት ቦታ አለ። በመሃከላቸው የተሰመረ የሚመስልህን ቀይ መስመር ስታልፍ ከአንደኛው ክልል ወደሌላኛው አልተሻገርክም። ጊዜ፣ ቦታና ሁኔታ…… ምናልባትም ሌላ ተጨማሪ ገቢር ትርጉማቸውን ያፋልሰዋል።
የሆነውን ለመረዳት(ለመዳኘት አላልኩም) ከነዚህ ሁለት ተቃራኒ ፅንፍ ከሚመስሉ ሀሳቦች መሃከል በሀሳባችን በምናሰምረው መሃል መስመር ላይ እንቁም! ወደየትኛውም እቅፍ ተጠግተን አንሙቅ።
እናማ የሆነው እንዲህ ነው…………
አንድ
የውብ ዳር አባቴን እና እናቴን ለያይታ አባቴን ያገባችው ስላፈቀረችው አልነበረም። ለበቀል እንጂ! የውብዳርና እማዬ ከልጅነት ጀምሮ ጓደኛሞች ነበሩ። የውብዳር ወንድም ያፈቀራትን እናቴን ማግባት የነፍስም የስጋም ፍፃሜያዊ ትልሙ ነበር። እና እናቴ ከአባቴ ጋር ፍቅር ስትጀምር ለምናልባቱ ያስቀመጡት የባይሆን ጭላንጭል የሌላቸው ስጋና ነፍሱ አድመው በዚህ ዓለም ዓለመኖርን መረጡ። የውብዳር ለብቸኛ ታላቅ ወንድሟ መርዝ ጠጥቶ መሞት ተጠያቂዋ ጓደኛዋ መሆኗን ብታምንም በራሷ እጅ ፍትህን ካላደረገች በቀር በየትኛውም ህግ እንደማትዳኝ ታውቃለች። (እዚህጋ የእማዬን ሚና በትክክል አላውቅም። ‘ከዳችው’ የሚለውን የየውብዳርን ቃል ወይም ‘ምንም አልነበረንም’ የሚለውን የእማዬን ቃል የትኛውን እንደማምን አላውቅም።) የሆነው ሆነና እናትና አባቴ ሲጋቡ የእናቴ ሚዜዋ የውብዳር ነበረች። በዓል ሆኖ እኛ ቤት ያልመጣችበት ቀን የለም።(እናቴ ስራ የሆነችባቸውን በዓላት የእመቤትነት ስርዓቱን የምትከውነው እሷ ነበረች።) እኔ ወይ አባዬ ታመን እማዬ ከሌለች እያደረች የምታስተዳድረን እሷ ነበረች። ልደቴ ሲከበር የሚያጓጓኝ የእርሷ ስጦታ ነበር። በቤታችን የፎቶ አልበም ውስጥ እሷ የሌለችበት ፎቶ ውስን እንደሆነው ሁሉ በኑሯችን ውስጥም እሷ የሌለችበት ገፅ ውስን ነበር።
ዘጠኝ ዓመት እስኪሆነኝ ድረስ አባትና እናቴ ሲሳሳሙ ወይ ሲላፍ ደርሼባቸው በሀፍረት ጉንጫቸው ቀልቶ አስደንግጫቸው ይሆናል እንጂ ተጣልተው ሲጨቃጨቁ ከእንቅልፌ ነቅቼ ያውም እናቴ አባቴን በጥፊ ስትለው አይቼ በመጮሄ አስደንግጫቸው አላውቅም። በሰዓቱ የፀቡ መንስኤ እማዬ ፓንት መኝታ ቤት ማግኘቷ መሆኑን ብሰማም አባዬ ከየውብዳር ጋር መማገጡን እሱ ከሰጠኝ ደብዳቤዎች ነው የተረዳሁት። (በደብዳቤው ላይ ጠጥቶ እንደነበር እና ስህተት እንደሆነ ፅፎ ይቅርታ ይለምናታል። የውብዳር ፓንቷን መኝታ ቤት ጥላ መሄዷ ያሰበችበት ተንኮል ነበረ።) ከዚህ በኋላ በብዙ ላብና እድሜ የከመሩትን ጡብ በአንድ ቀን እንደማፍረስ ሁሉ ቤታችን የፈረሰው ተምዘግዝጎ ነበር። እማዬ የበለጠ የጎዳት ከሌላ ሴት ጋር መተኛቱ አይደለም። ከምትወዳት ጓደኛዋ ጋር መተኛቱ እንጂ…… የየውዳር በቀል የገባት ሲቆይ ነው።
እዚህ ተረክ ውስጥ ማናቸውም ጥሩ አይደሉም። ማናቸውም ክፉ አይደሉም። እንደማንኛውም ሰው ባበዙት ይጠሩበታል። ቤታችን በየእለቱ ጭቅጭቅ ሆነ። እማዬ አባቴን ጥላ ከእኔጋ ማደር ጀመረች። በነዚህ ሁሉ ጊዜያት የይቅርታ ደብዳቤ ፅፎላታል። ብዙም ሳይቆይ የውብዳር ማርገዟ ታወቀ። እናቴ ከልጁና ከእሷ እንዲመርጥ ነገረችው። ይሄን ከሰማች በኋላ እማዬ አንድ ቀን ከስራ ውጪ ሌላ ቦታ አደረች። ከሌላ ሰው ጋር… … አባቴ አወቀ። …… የአባቴ በደል ወይስ የራሷ ፀፀት አላውቅም ብዙ ሳይቆይ በአዕምሮ መታወክ ስራዋን አጣች። እህቷ ፀበል ይዛት ትኳትን ጀመር። አባቴ መምረጥ ነበረበት። እብድ ሚስቱን ወይም በፍቅርህ ሞትኩ የምትለውን የውብዳርን፤ በደሏን በራሱ በደል አጣፍቶ ይቅር ማለት እና ከእናቴ ጋር መኖር (ይሄ ያልተወለደች ልጁን ችላ ማለትን ያካትታል።) ወይም አዲስ ህይወት መጀመር።
አየህ ክልል ብሎ ፍልስፍና እንደሌለ? ያበደች ሚስቱን ትቶ ገና ተወልዳ ያላያትን ልጁን መምረጥ ልክ አይደለም። ለፍቅሩና ለሚስቱ አድልቶ በእነርሱ በደል ምንም የማታውቀውን ልጁን ቤተሰብ መንሳትም ልክ አይሆንም። ግድ ሲሆን ግን ከሁለት ስህተት አንዱን ስህተት መምረጥ ልክ ይሆናላ!
ትልቅ የሚባል ስኬት ፣ ፍፁም የሚባል ፍቅር ፣ ግዙፍ የሚባል እምነት ፣ የማይረታ የሚባል አንድነት…… ለመውደቅ ‘ትልቅ ምክንያት’ ሊያንገዳግደው ግድ አይደለም። ብዙ ትንሽ ምክንያቶች ከስሩ መንግለው ይደፉታል።
ሁለት
ቤተሰቦቼ በራሳቸው ጡዘት ሲጦዙ ዕጣ ፈንታዬ ምን እንደሚሆን አርቀው ያላሰቡልኝ እኔ እነርሱ በበሉት የተበላሸ ምግብ እኔ ስቀዝን ኖርኩ። እነርሱ በበሉት የተበላሸ ፍሬ የእኔ ጥርስ በለዘ። እናቴ በከፊል ጤነኛ በሆነ ጭንቅላቷ በከፊል በእህቷ ጭንቅላት ከአባቴ ጋር ላለመኖር ወሰነች። አባቴ የውብዳርን አገባ። ከአባቴ እና ከእንጀራ እናቴጋ ሁለት ዓመት ኖርኩ። ያጣሁት እናቴን ብቻ አልነበረም። አባቴም በዝምታና በድባቴ የተከበበ እኔ ከማውቀው ሳቅና ፍቅር ከሞላው አባቴ የተለየ ሌላ ሰው ሆነ። አብዛኛውን ምሽት አምሽቶ ጠጥቶ ስለሚገባ አላገኘውም። የቤቱ አዛዥ ሚስቱ ናት! እሱ ደግሞ ለሚሆነው ሁሉ መልሱ ዝምታ ነው። አክስቴ ስትወስደኝ ሚስቱ ምን ያህል እንደምትከፋብኝ ስለሚያውቅ አባቴ አልተቃወመም።
እዚህጋ ስህተትም ልክም ፅድቅም ሀጢያትም… … መልካምነትም ክፋትም… … ሁሉም ቦታ የላቸውም። ምክንያቱም ለእነዚህ ሁሉ ክስተቶች አንዲት ጥሬ ዘር ያላበረከትኩ እኔ ጎተራ ሙሉ መራራ ፍሬ ሳጭድ በየትኛው ሚዛን ተዳኝቶ ከአንዳቸው ይመደባል?
“ብትጠይኝ አልፈርድብሽም። በዚህ ሁሉ ነገር ውስጥ የተጎዳሽው አንቺ ነሽ።” አለኝ አባቴ ከዘመናት በኋላ ዛሬ ላይ
“ስለእውነት እንደክህደትህ ብጠላህ ደስ ይለኛል። ከቤትህ አውጥተህ እንደጣልከው ቆሻሻ ስለረሳኸኝ አስከፍልህ ነበር። እድሜ ለእናቴ በል በሷ ልብ ውስጥ ስላነገሰችው ማንነትህ ስል እንደማንኛውም በህይወቴ ትርጉም እንደሌለው ሰው ቆጥሬሃለሁ።”
“ምንም ብልሽ ላንቺ በቂ የሚሆን ምክንያት ልሰጥሽ አልችልም ግን አልከዳሁሽም አንድም ቀን ረስቼሽም አላውቅም አንቺንም ሆነ እናትሽን እንዳላያችሁ አክስትሽ በህግ አስከልክላኛለች። አንቺን ከእናትሽ መንጠቁ ደግሞ
እናትሽን እንደመግደል ነበር።”
አያችሁ…ትልቅ ምክንያት አያስፈልግም። አባት ልጁን ለመተው እንኳን ቢሆን ትንንሽ ብዙ ምክንያቶች ሀያል ጉልበት አላቸው እናቴን በማጣቱ መጎዳቱ፣ሌላኛዋንም ልጁን
:
#ክፍል_አስር
:
✍ደራሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
:
...የገዛ ሚስትህ በአደባባይ አብረሃት እየሄድክ ጡቶቿን የከለላቸውን ጨርቆች ገፋ ሳምልኝ ብትልህ ብልግና ይሆንብሃል። በሷ ድርጊት አንተ ትሸማቀቃለህ። መኝታ ቤታችሁ ውስጥ ራቁቷን ሆና ያንኑ ነገር ብትልህ ለቦታው የሚገባ ቅድስና አድርገህ ልትቆጥረው ትችላለህ። ምናልባትም ከዛ በላይ ‘ስድ’ ብትሆንልህ ያምርሃል።
በመንፈሳዊው ዓለም የመጀመሪያው ለሰው ልጆች የተሰጠ የተፃፈ ህግ አስርቱ ትዕዛዛት ናቸው። አትግደል የሚል ህግ ፅፎ ሰጥቷቸዋል። ጠላት በተነሳባቸው ጊዜ ግን አሳልፌ ሰጥቻችኋለሁና ዝመቱባቸው ብሎ እልፎች ያስገድላል።
በምድረኛው ህግም መግደል ወንጀል ነው ይልሃል። አንዳንድ ወንጀሎች ግን በዛው ህግ በሞት ያስቀጣሉ። እናም ፍትህ ነው ይልሃል። በተመሳሳይ በቀል ሀጢያት ነው ይሉሃል። የበደለህን ሰው አስጠፍንገህ ወህኒ ማስወርወር ግን በቀል ሳይሆን ፍትህ ነው ትባላለህ። ምናልባት አንተም ከዛ በላይ የምታደርገው ላይኖር ይችል ይሆናል እኮ!
አየህ በዚህኛው አለም ስትኖር ሀጢያት ወይ ፅድቅ፣ ልክ ወይ ስህተት፣ መልካም ወይም ክፉ፣ ብልግና ወይ ጨዋነት… እነዚህ አንዱ ከሌላኛው ተቃራኒ ዋልታ የሚገኝ መቼም የማይስማሙ ሊመስል ይችላል። አይደለም! እንደውም አንዱ በአንደኛው የሚተካካበት ቦታ አለ። በመሃከላቸው የተሰመረ የሚመስልህን ቀይ መስመር ስታልፍ ከአንደኛው ክልል ወደሌላኛው አልተሻገርክም። ጊዜ፣ ቦታና ሁኔታ…… ምናልባትም ሌላ ተጨማሪ ገቢር ትርጉማቸውን ያፋልሰዋል።
የሆነውን ለመረዳት(ለመዳኘት አላልኩም) ከነዚህ ሁለት ተቃራኒ ፅንፍ ከሚመስሉ ሀሳቦች መሃከል በሀሳባችን በምናሰምረው መሃል መስመር ላይ እንቁም! ወደየትኛውም እቅፍ ተጠግተን አንሙቅ።
እናማ የሆነው እንዲህ ነው…………
አንድ
የውብ ዳር አባቴን እና እናቴን ለያይታ አባቴን ያገባችው ስላፈቀረችው አልነበረም። ለበቀል እንጂ! የውብዳርና እማዬ ከልጅነት ጀምሮ ጓደኛሞች ነበሩ። የውብዳር ወንድም ያፈቀራትን እናቴን ማግባት የነፍስም የስጋም ፍፃሜያዊ ትልሙ ነበር። እና እናቴ ከአባቴ ጋር ፍቅር ስትጀምር ለምናልባቱ ያስቀመጡት የባይሆን ጭላንጭል የሌላቸው ስጋና ነፍሱ አድመው በዚህ ዓለም ዓለመኖርን መረጡ። የውብዳር ለብቸኛ ታላቅ ወንድሟ መርዝ ጠጥቶ መሞት ተጠያቂዋ ጓደኛዋ መሆኗን ብታምንም በራሷ እጅ ፍትህን ካላደረገች በቀር በየትኛውም ህግ እንደማትዳኝ ታውቃለች። (እዚህጋ የእማዬን ሚና በትክክል አላውቅም። ‘ከዳችው’ የሚለውን የየውብዳርን ቃል ወይም ‘ምንም አልነበረንም’ የሚለውን የእማዬን ቃል የትኛውን እንደማምን አላውቅም።) የሆነው ሆነና እናትና አባቴ ሲጋቡ የእናቴ ሚዜዋ የውብዳር ነበረች። በዓል ሆኖ እኛ ቤት ያልመጣችበት ቀን የለም።(እናቴ ስራ የሆነችባቸውን በዓላት የእመቤትነት ስርዓቱን የምትከውነው እሷ ነበረች።) እኔ ወይ አባዬ ታመን እማዬ ከሌለች እያደረች የምታስተዳድረን እሷ ነበረች። ልደቴ ሲከበር የሚያጓጓኝ የእርሷ ስጦታ ነበር። በቤታችን የፎቶ አልበም ውስጥ እሷ የሌለችበት ፎቶ ውስን እንደሆነው ሁሉ በኑሯችን ውስጥም እሷ የሌለችበት ገፅ ውስን ነበር።
ዘጠኝ ዓመት እስኪሆነኝ ድረስ አባትና እናቴ ሲሳሳሙ ወይ ሲላፍ ደርሼባቸው በሀፍረት ጉንጫቸው ቀልቶ አስደንግጫቸው ይሆናል እንጂ ተጣልተው ሲጨቃጨቁ ከእንቅልፌ ነቅቼ ያውም እናቴ አባቴን በጥፊ ስትለው አይቼ በመጮሄ አስደንግጫቸው አላውቅም። በሰዓቱ የፀቡ መንስኤ እማዬ ፓንት መኝታ ቤት ማግኘቷ መሆኑን ብሰማም አባዬ ከየውብዳር ጋር መማገጡን እሱ ከሰጠኝ ደብዳቤዎች ነው የተረዳሁት። (በደብዳቤው ላይ ጠጥቶ እንደነበር እና ስህተት እንደሆነ ፅፎ ይቅርታ ይለምናታል። የውብዳር ፓንቷን መኝታ ቤት ጥላ መሄዷ ያሰበችበት ተንኮል ነበረ።) ከዚህ በኋላ በብዙ ላብና እድሜ የከመሩትን ጡብ በአንድ ቀን እንደማፍረስ ሁሉ ቤታችን የፈረሰው ተምዘግዝጎ ነበር። እማዬ የበለጠ የጎዳት ከሌላ ሴት ጋር መተኛቱ አይደለም። ከምትወዳት ጓደኛዋ ጋር መተኛቱ እንጂ…… የየውዳር በቀል የገባት ሲቆይ ነው።
እዚህ ተረክ ውስጥ ማናቸውም ጥሩ አይደሉም። ማናቸውም ክፉ አይደሉም። እንደማንኛውም ሰው ባበዙት ይጠሩበታል። ቤታችን በየእለቱ ጭቅጭቅ ሆነ። እማዬ አባቴን ጥላ ከእኔጋ ማደር ጀመረች። በነዚህ ሁሉ ጊዜያት የይቅርታ ደብዳቤ ፅፎላታል። ብዙም ሳይቆይ የውብዳር ማርገዟ ታወቀ። እናቴ ከልጁና ከእሷ እንዲመርጥ ነገረችው። ይሄን ከሰማች በኋላ እማዬ አንድ ቀን ከስራ ውጪ ሌላ ቦታ አደረች። ከሌላ ሰው ጋር… … አባቴ አወቀ። …… የአባቴ በደል ወይስ የራሷ ፀፀት አላውቅም ብዙ ሳይቆይ በአዕምሮ መታወክ ስራዋን አጣች። እህቷ ፀበል ይዛት ትኳትን ጀመር። አባቴ መምረጥ ነበረበት። እብድ ሚስቱን ወይም በፍቅርህ ሞትኩ የምትለውን የውብዳርን፤ በደሏን በራሱ በደል አጣፍቶ ይቅር ማለት እና ከእናቴ ጋር መኖር (ይሄ ያልተወለደች ልጁን ችላ ማለትን ያካትታል።) ወይም አዲስ ህይወት መጀመር።
አየህ ክልል ብሎ ፍልስፍና እንደሌለ? ያበደች ሚስቱን ትቶ ገና ተወልዳ ያላያትን ልጁን መምረጥ ልክ አይደለም። ለፍቅሩና ለሚስቱ አድልቶ በእነርሱ በደል ምንም የማታውቀውን ልጁን ቤተሰብ መንሳትም ልክ አይሆንም። ግድ ሲሆን ግን ከሁለት ስህተት አንዱን ስህተት መምረጥ ልክ ይሆናላ!
ትልቅ የሚባል ስኬት ፣ ፍፁም የሚባል ፍቅር ፣ ግዙፍ የሚባል እምነት ፣ የማይረታ የሚባል አንድነት…… ለመውደቅ ‘ትልቅ ምክንያት’ ሊያንገዳግደው ግድ አይደለም። ብዙ ትንሽ ምክንያቶች ከስሩ መንግለው ይደፉታል።
ሁለት
ቤተሰቦቼ በራሳቸው ጡዘት ሲጦዙ ዕጣ ፈንታዬ ምን እንደሚሆን አርቀው ያላሰቡልኝ እኔ እነርሱ በበሉት የተበላሸ ምግብ እኔ ስቀዝን ኖርኩ። እነርሱ በበሉት የተበላሸ ፍሬ የእኔ ጥርስ በለዘ። እናቴ በከፊል ጤነኛ በሆነ ጭንቅላቷ በከፊል በእህቷ ጭንቅላት ከአባቴ ጋር ላለመኖር ወሰነች። አባቴ የውብዳርን አገባ። ከአባቴ እና ከእንጀራ እናቴጋ ሁለት ዓመት ኖርኩ። ያጣሁት እናቴን ብቻ አልነበረም። አባቴም በዝምታና በድባቴ የተከበበ እኔ ከማውቀው ሳቅና ፍቅር ከሞላው አባቴ የተለየ ሌላ ሰው ሆነ። አብዛኛውን ምሽት አምሽቶ ጠጥቶ ስለሚገባ አላገኘውም። የቤቱ አዛዥ ሚስቱ ናት! እሱ ደግሞ ለሚሆነው ሁሉ መልሱ ዝምታ ነው። አክስቴ ስትወስደኝ ሚስቱ ምን ያህል እንደምትከፋብኝ ስለሚያውቅ አባቴ አልተቃወመም።
እዚህጋ ስህተትም ልክም ፅድቅም ሀጢያትም… … መልካምነትም ክፋትም… … ሁሉም ቦታ የላቸውም። ምክንያቱም ለእነዚህ ሁሉ ክስተቶች አንዲት ጥሬ ዘር ያላበረከትኩ እኔ ጎተራ ሙሉ መራራ ፍሬ ሳጭድ በየትኛው ሚዛን ተዳኝቶ ከአንዳቸው ይመደባል?
“ብትጠይኝ አልፈርድብሽም። በዚህ ሁሉ ነገር ውስጥ የተጎዳሽው አንቺ ነሽ።” አለኝ አባቴ ከዘመናት በኋላ ዛሬ ላይ
“ስለእውነት እንደክህደትህ ብጠላህ ደስ ይለኛል። ከቤትህ አውጥተህ እንደጣልከው ቆሻሻ ስለረሳኸኝ አስከፍልህ ነበር። እድሜ ለእናቴ በል በሷ ልብ ውስጥ ስላነገሰችው ማንነትህ ስል እንደማንኛውም በህይወቴ ትርጉም እንደሌለው ሰው ቆጥሬሃለሁ።”
“ምንም ብልሽ ላንቺ በቂ የሚሆን ምክንያት ልሰጥሽ አልችልም ግን አልከዳሁሽም አንድም ቀን ረስቼሽም አላውቅም አንቺንም ሆነ እናትሽን እንዳላያችሁ አክስትሽ በህግ አስከልክላኛለች። አንቺን ከእናትሽ መንጠቁ ደግሞ
እናትሽን እንደመግደል ነበር።”
አያችሁ…ትልቅ ምክንያት አያስፈልግም። አባት ልጁን ለመተው እንኳን ቢሆን ትንንሽ ብዙ ምክንያቶች ሀያል ጉልበት አላቸው እናቴን በማጣቱ መጎዳቱ፣ሌላኛዋንም ልጁን
👍8
እንደእኔ የተመሳቀለ ህይወት እንዳይኖራት ለመከላከል፣ የአክስቴ ሀይለኛነት፣ የእኔ እማዬጋ ለመኖር መፈለግ፣ የእንጀራ እናቴ ክፋት……… አንዳቸው ለብቻቸው ምንም የማይሆኑ ሲደማመሩ በኔና በሱ መሀከል ያለውን ትስስር መበጠስ የቻሉ ምክንያቶች ናቸው። አሁን ደግሞ ሚስቱን ሊፈታት ነው። ምክንያቱ ልጁ ስላገባች ከየውዳር ጋር የሚያኖር ምክንያት እንደሌለው ስለሚያስብ።
“ይቅርታ ልጄ! አሁን ይቅርታዬ ያለፍሽበትን ነገር እንደማይሽር አውቃለሁ። አስቤሽ ሁሌም እንደምታመም ግን እወቂ።”
“አሁን ዋናው ነገር የእማዬ ደስታ ነው። በቀራት ጊዜ ደስተኛ እንድትሆንልኝ እፈልጋለሁ።” አልኩት አንድ ቀን መጥቶ ይጠይቀኛል ብዬ የጠበቅኳቸው ቀናት እንዳልነበሩ፣ ከእኔና ከእናቴ የውዳርንና እህቴን በመምረጡ በእህቴ እንዳልቀናሁ፣ እነርሱን ትቶ ከእኛጋር እንዲኖር ልለምነው አስቤ እንደማላውቅ…………
ሶስት
ፍትህ ፍርዱ ልክ እንዳልሆነ እያወቀ ትዝታ 25 ዓመት ሲፈረድባት እጅ ሰጥቶ መቀመጥን መረጠ። ምክንያቱ ደግሞ የነበረው ምርጫ ማሸነፍ ወይ መሸነፍ አልነበረም። ይሄ ቀሽም የአንደኛ ደረጃ መምህር ያዘጋጀው ዓይነት ምርጫ ቀላል በሆነለት ነበር። ሁለት የማይመረጡ ምርጫዎች ነበሩት። ትዝታን ማዳን ወይ ቤተሰቡን ማዳን!! ትዝታን መርጦ ከሚወዳቸው አንዳችንን ማጣት ለእርሱ በምንም ስሌት ልክ አይሆንም። የሚወዳቸውን መርጦ ትዝታን መክዳትም በሂሳብም በሳይንስም ልክ አይሆንም። አየህ ድንበር ብሎ ፈሊጥ እንደሌለ? ግድ ሲሆን ከሁለት ስህተት አንዱን ስህተት መምረጥ ልክ የሚሆንበት አጋጣሚ ይፈጠራል። ቆይ ቆይ…… እንዲህ ቀላልና ምክንያታዊ ውሳኔ አልነበረም። ሁላችንንም ዋጋ ያስከፈ እንጂ……
እንደውም ትዝታን ማዳን የሚለው ምርጫ አይደለም። ትዝታ መዳን አትፈልግም። ደፍሯታል ወይም አታሏታል…… ልጅን ያህል ነገር ወልዳለች። ለምን ለዚህ ሰው ትከላከልለታለች? የልጇ አባት አጎቷ መሆኑን ፍትህ ሲጠይቃት ድንጋጤዋ እውነቱን ቢያሳብቅባትም ካደች።
“በቅቶኛል። ራሁ ይህቺ ልጅ ምንም መስዋዕትነት የሚገባት አይደለችም።” አለኝ ፍትህ።
“ፍትህ ለእርሷ ብለህ ነው ወይስ ለሙያህ? ለእውነት? ለፍትህ?”
“የሆነ ሰው አርፌ ካልተቀመጥኩ አንቺን፣ ካስዬን ወይ እማዬን እንደሚያስከፍለኝ አስጠንቅቆኛል። ማስፈራሪያ ብቻ አይደለም።” አለኝ በሰጋ ልብ። እሱ ይሄን ከማለቱ ከአንድ ሰዓት በፊት የማላውቀው ሰው ሆስፒታሉ መግቢያ ጋር አስቁሞኝ ተመሳሳይ ማስጠንቀቂያ ለእኔም ሰጥቶኛል።
🌑ይቀጥላል➡️
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ ያበረታናልና 👍
Like👍 እያደረጋቹ
አስተያየት ካሎ በ @atronosebot አድርሱን
“ይቅርታ ልጄ! አሁን ይቅርታዬ ያለፍሽበትን ነገር እንደማይሽር አውቃለሁ። አስቤሽ ሁሌም እንደምታመም ግን እወቂ።”
“አሁን ዋናው ነገር የእማዬ ደስታ ነው። በቀራት ጊዜ ደስተኛ እንድትሆንልኝ እፈልጋለሁ።” አልኩት አንድ ቀን መጥቶ ይጠይቀኛል ብዬ የጠበቅኳቸው ቀናት እንዳልነበሩ፣ ከእኔና ከእናቴ የውዳርንና እህቴን በመምረጡ በእህቴ እንዳልቀናሁ፣ እነርሱን ትቶ ከእኛጋር እንዲኖር ልለምነው አስቤ እንደማላውቅ…………
ሶስት
ፍትህ ፍርዱ ልክ እንዳልሆነ እያወቀ ትዝታ 25 ዓመት ሲፈረድባት እጅ ሰጥቶ መቀመጥን መረጠ። ምክንያቱ ደግሞ የነበረው ምርጫ ማሸነፍ ወይ መሸነፍ አልነበረም። ይሄ ቀሽም የአንደኛ ደረጃ መምህር ያዘጋጀው ዓይነት ምርጫ ቀላል በሆነለት ነበር። ሁለት የማይመረጡ ምርጫዎች ነበሩት። ትዝታን ማዳን ወይ ቤተሰቡን ማዳን!! ትዝታን መርጦ ከሚወዳቸው አንዳችንን ማጣት ለእርሱ በምንም ስሌት ልክ አይሆንም። የሚወዳቸውን መርጦ ትዝታን መክዳትም በሂሳብም በሳይንስም ልክ አይሆንም። አየህ ድንበር ብሎ ፈሊጥ እንደሌለ? ግድ ሲሆን ከሁለት ስህተት አንዱን ስህተት መምረጥ ልክ የሚሆንበት አጋጣሚ ይፈጠራል። ቆይ ቆይ…… እንዲህ ቀላልና ምክንያታዊ ውሳኔ አልነበረም። ሁላችንንም ዋጋ ያስከፈ እንጂ……
እንደውም ትዝታን ማዳን የሚለው ምርጫ አይደለም። ትዝታ መዳን አትፈልግም። ደፍሯታል ወይም አታሏታል…… ልጅን ያህል ነገር ወልዳለች። ለምን ለዚህ ሰው ትከላከልለታለች? የልጇ አባት አጎቷ መሆኑን ፍትህ ሲጠይቃት ድንጋጤዋ እውነቱን ቢያሳብቅባትም ካደች።
“በቅቶኛል። ራሁ ይህቺ ልጅ ምንም መስዋዕትነት የሚገባት አይደለችም።” አለኝ ፍትህ።
“ፍትህ ለእርሷ ብለህ ነው ወይስ ለሙያህ? ለእውነት? ለፍትህ?”
“የሆነ ሰው አርፌ ካልተቀመጥኩ አንቺን፣ ካስዬን ወይ እማዬን እንደሚያስከፍለኝ አስጠንቅቆኛል። ማስፈራሪያ ብቻ አይደለም።” አለኝ በሰጋ ልብ። እሱ ይሄን ከማለቱ ከአንድ ሰዓት በፊት የማላውቀው ሰው ሆስፒታሉ መግቢያ ጋር አስቁሞኝ ተመሳሳይ ማስጠንቀቂያ ለእኔም ሰጥቶኛል።
🌑ይቀጥላል➡️
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ ያበረታናልና 👍
Like👍 እያደረጋቹ
አስተያየት ካሎ በ @atronosebot አድርሱን
👍3🥰1
#ራሴው_ማበዴ_ነው (የመጨረሻ ክፍል)
:
#ክፍል_አስራ_አንድ
:
✍ደራሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
:
...አልነገርኩትም። የማላውቀው ሰው የሆስፒታሉ መግቢያ በርጋ ጠብቆኝ የትዝታን ጉዳይ ማነፍነፍ ካላቆምኩ ከምወዳቸው ሰዎች አንዳቸውን እንደማጣ እንዳስጠነቀቀኝ አልነገርኩትም። ብዙ ነገር አልነገርኩትም። እንዲያውም ምንም አልነገርኩትም። እማዬ ከዚህ በኋላ ህክምና የሚፈይድላት ነገር ስለሌለ ወደቤቷ ወስደናት ዓይን ዓይኗን እያየሁ የምትሞትበትን ቀን መጠበቅ ትኩስ ቁስል ላይ ሚጥሚጣ እንደመበተን እየለበለበኝ እንደሆነ አልነገርኩትም። እቅፉ ውስጥ ሆኜ እዬዬ ብዬ ማልቀስ እንደምፈልግም። ከሰሞኑ አባቴን ሆስፒታል በማድረስ ሰበብ አዘውትረው ሲመጡ እህቴና ባሏን ማየት ልቤን በደም ፈንታ ቅናት እንደሚያስረጨው አልነገርኩትም። በእኔና በእርሱ መሃል ምንም ነገር እንደሌለ የሚሆነው መሆን እየከፋኝ አልቅሺ አልቅሺ እንደሚለኝ አልነገርኩትም። በዚህ ሁሉ ማጥ ውስጥ አቅፎኝ ያደረ ቀን የማግኩት ጠረኑን እርሱ አጠገቤ ሳይኖር እንኳን ካለበት ንፋሱ እያንጓለለ ለአፍንጫዬ እንደሚያቀብለው አልነገርኩትም። አጠገቤ ሆኖ ስለስራ እያወራኝ ልነካው እንደምፈልግ፣ ልስመው እንደምጎመዥ፣ እርሱ የኔ ቢሆንና በፈለግኩት ቁልምጫ ልጠራው እንደምመኝ… … አልነገርኩትም።]
“ማንናቸው?” አለኝ ዓይኔን ተከትሎ መኪና ውስጥ ያሉትን እህቴንና ባሏን እያያቸው
“እህምም…… እህቴ ናት! ባሏ ነው። አባቴን ወደቤት ሊያደርሱት እየጠበቁት ነው።” አልኩት አንገቴን ሰብሬ
“ታዲያ ምን?” አለኝ ዓይኔን እየፈለገ
“ምን?”
“ለምንድነው ስታያቸው በነበረው እይታ የምታያቸው? ምንድነው እሱ?”
“ኸረ ምንም አይደለም። በቃ ከእህቴ ጋር ስለማንነጋገር ነው።”
“አይደለም ራሁ። እያየሁሽ እኮ ነው። ቆይ ምንባደርግ ነው የተሰማሽን ልትነግሪኝ የምታምኚኝ? የበለጠ የቀረብኩሽ በመሰለኝ ቁጥር ለአካልሽ እንጂ ለልብሽ አልቀርብሽም። አብሬሽ ውዬ ባድር ቅርበቴ አይሰማሽም።…”
“ፍቅረኛዬ ነበረ። እህቴ ያገባችው ሰው…” ወቀሳውን እንዲያቆምልኝ ይሆን ለልቤ መቅረቡን እንዲያውቅልኝ አላውቅም። ነገርኩት!!
[ ዘጠነኛ ክፍል ስገባ አንድ ወንበር ላይ ከተቀመጥን ጀምሮ ብቸኛ ጓደኛዬ ዓለማየሁ እንደነበረ ግን አልነገርኩትም። የአስረኛ ክፍል ፈተና ተፈትነን ከተማሪዎች ጋር ከከተማ የወጣን ጊዜ ከንፈሬን ሲስመኝ ከርሱ ውጪ ያለውን ዓለም እንደረሳሁ አልነገርኩትም። በመከራ ከተከበበው ኑሮዬ የተረፈኝን ሰዓት ከርሱ ጋር ማሳለፌ በነገ ተስፋ እንዳልቆርጥ መፅናኛዬ ሆኖ በጥሩ ውጤት አብረን ዩንቨርስቲ እንደገባን አልነገርኩትም። ብዙ ጊዜ ‘ድብቅ ነሽ አላውቅሽም’ እያለ ቢነጫነጭም ይተወኛል ብዬ ለአፍታ አስቤ ባለማወቄ ሲተወኝ ከእማዬጋ አብሬ ማበድ ዳድቶኝ እንደነበረም አልነገርኩትም። የባሰው ደግሞ ከዓመታት በኋላ እሱ ዩንቨርስቲ አስተማሪ ሆኖ ተማሪው ከሆነችው እህቴ ጋር በአጋጣሚ ይሁን አስቦበት እስከአሁንም በማይገባኝ ሁናቴ ግንኙነት መጀመራቸውን ሆነ ብሎ ደውሎ የነገረኝ ማታ ራሴን ልስት እንደነበረ አልነገርኩትም። እህቴ ከዩንቨርስቲ በተባረረች በወራት ውስጥ የሰርጋቸው ጥሪ ካርድ ሲደርሰኝ ራሴን ባለመፈለግ ስሜት ውስጥ አዝቅጬው መብሰክሰኬን አልነገርኩትም። ከዓለማየሁ በፊትም በኋላም ሌላ ፍቅር እንደማላውቅም አልነገርኩትም።]
“እና አሁንም ድረስ ትወጂዋለሽ? እየቀናሽ ነው?” አለኝ
“አይይይ ለሱ ምንም ስሜት የለኝም። በሱ አልቀናም።”
“በሷ?” እያለኝ በጣም ተጠጋኝ። ትንፋሹ ጉንጮቼ ላይ እያቃጠለኝ አስቤ የተሰደሩ ቃላት መናገር አልችልም ነበር። በጭንቅላቴ ንቅናቄ ‘አዎን’ አልኩት። አልበቃውም እንድቀጥልለት ይጠብቃል። ምራቄ እያነቀኝ ነው።
“አባቴ ከእኔ እሷን ነበር የመረጠው። ፍቅረኛዬም… …” አላስጨረሰኝም ከንፈሬን በከንፈሩ ከደነው። መሳሙ ቀለምም ነበረው፣ ሽታም ነበረው፣ ጣዕምም ነበረው……
“በሚፈጠሩ ክስተቶች ውስጥ ራስሽን እየከተትሽ አትስፈሪ። ሁኔታዎች ሁሉ አንቺን ሚዛን ላይ አስቀምጠው አይለኩም።” አለኝ ለምን ያህል ደቂቃ እንደሆነ ስሞኝ ሲያበቃ… … ሰምቼዋለሁ? ገብቶኛልስ? መሳሙን እያጣጣምኩ ነበር።
“ተያቸው! እርሻቸው!” አለኝ ወደእነእህቴ እያየ። እያየኋቸው ነበር። የልጅ ስሜት ቢመስልም አዎን ሲስመኝ ማየታቸውን ለማረጋገጥ ነበር የማያቸው። አለ አይደለ እኔም ሰው አለኝ አይነት! አልጎዳችሁኝም አይነት! እንዳዩኝ በማወቄም በከፊል የታባታችሁ አይነት ስሜት……
በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ብዙ ነገር ተቀየረ። እንደውም ሁሉም ነገር!! እማዬ ወደቤት መጣች። ካስዬና አባቴ እቤታችን እየመጡ እናቴን መጠየቅ ጀመሩ። እኔና ፍትህ ቤተሰቦቻችን እስኪያውቁ እንደፍቅረኛሞች ገብተን መውጣት ጀመርን። ፍትህ የትዝታን ጉዳይ ተለዋጭ ቀጠሮ ሊጠይቅ በተዘጋጀበት ወቅት እጅ ያሰጠው ሁናቴ ተፈጠረ። አባቴ ሞቶ ተገኘ።
ቆይ ቆይ ፍትህ በትዝታ ጉዳይ ተስፋ መቁረጡ እና 25 ዓመት ሲፈረድባት መዋጡ ቀላል አልነበረም። ቤተሰቡን በሙሉ ያስከፈለ መስዋዕትነት እንጂ… …… ካልንበት እንቀጥል። አባቴ ተገደለ! ይቅርታ እንዳደርግለት ሲለማመጠኝ የነበረው አባቴ አንድስ እንኳን በጎ ቃል ሳልነግረው ሞተ። በራሴው ጉዳይ እርሱ አንዲት ጠጠር ባላበረከተበት የነገር ካብ ህይወቱን አጣ!! ለፍትህ ይሄ የመጀመሪያው መሆኑ እና ካላረፈ ሌሎቻችንም ተራ ጠባቂዎች መሆናችን እና ቀጣይዋ እኔ መሆኔ ማስጠንቀቂያ ደረሰው። ይሄኔ ነው እጅ የሰጠው! ከእኔ በላይ ሁሉ የተጎዳ መሰለኝ።
“በፍፁም አንቺን ለምርጫ ማቅረብ አልችልም። አንቺን ማጣት አልችልም።” ይለኛል እየደጋገመ። ለማን እንዳለቀሰ ያልገባኝን ለቅሶ በአባቴ ቀብር ላይ ምርር ብሎ አለቀሰ። ግራ የገባው ስሜት ውስጥ ጠለቅኩ። አንዱ አካሌ ሽባ የሆነ ነገር ይመስለኛል። ከሬሳው ጋር የቀበርኩት ነገር ያለ ይመስል የሆነ ስሜቴ ወደአባቴ መቃብር ይጎትተኛል።
የባሰው ነገር ለእናቴ የፍቅሯን ሞት ማርዳት ነበር። በየቀኑ እየመጣ ሲያያት የከረመውን ሰው በምንም ሰበብ ቀረ ልንላት አንችልም። እንደገና እንደተዋት በምንም ምክንያት ሰንገን ብንነግራት ጤነኛ አትሆንም። መሞቱንም ብታውቅ ጤነኛ አትሆንም። ቢያንስ ግን ከመከዳት ስሜት ፍቅረኛዋ እያፈቀራት መሞቱን ማወቋ ይሻላል በሚል ተስማምተን የተሻለ ሁኔታ ላይ ያለው ካስዬ ነገራት። ዝም አለች። ለሁለት ሰዓታት ዝም አለች። እኔን የምታይበትን መንገድ አልወደድኩትም። ያንቺ ጦስ ነው ፍቅሬን ያሳጣኝ አይነት መልዕክት አለው። ድንገት ከየት ባመጣችው ጉልበት እንደሆነ እንጃ ተስፈንጥራ ተነስታ ቀብሩን እሄዳለሁ ብላ አመሰችን። ካስሽ ይዟት ሄደ። ካስሽ ደግፏት ፍቅሯ አፈር ሲገባ አነባች። አለቃቀሷ ግጥምም ቃልም ሳይኖረው ዜማ አለው። እያየኋት ለአባቴ ይሁን ለእርሷ ብቻ አነባሁ! ስለእውነት የውብዳር እንኳን ስታለቅስ አሳዘነችኝ። በየመሃሉ ለሞቱ ተጠያቂ መሆኔን ልትነግረኝ አንዳንድ ሀረግ ትመዛለች። እህቴ አፈሩ ላይ ተልሞሰሞሰች። ትንፋሽ አጥሮኝ ደረቴ ላይ ሲያፍነኝ ነው ቀብሩ ያበቃው እና ወደቤታችን የተመለስነው።
እቤት ከመግባታችን እማዬ “ይሄ የበረራ ቁጥር… …” ማለት ጀመረች። መሬቷ ያንሳፈፈችኝ አይነት ስሜት ተሰማኝ። ግራቪቲ የከዳኝ! ያልበላሁት ምግብ ወደ ላይ ወደላይ አለኝ። እሪሪሪ ብዬ ማልቀስ እፈልጋለሁ። ግን ጉሮሮዬም ደረቴም የታፈነ ይመስለኛል።
“እኔ አለሁ አንቺ እረፊ!” አለኝ ካስዬ። እንዳለውም ከዚያን ቀን በኋላ ኖረ። ምክንያቱም በሚቀጥሉት ቀናት እናቴ ማነሽ? ማለት ጀመረች። ፍትህንም ስታይ መበርገግ ጀመረች። የሚገርመው ካስዬን በባሏ ስም አንድዬ
:
#ክፍል_አስራ_አንድ
:
✍ደራሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
:
...አልነገርኩትም። የማላውቀው ሰው የሆስፒታሉ መግቢያ በርጋ ጠብቆኝ የትዝታን ጉዳይ ማነፍነፍ ካላቆምኩ ከምወዳቸው ሰዎች አንዳቸውን እንደማጣ እንዳስጠነቀቀኝ አልነገርኩትም። ብዙ ነገር አልነገርኩትም። እንዲያውም ምንም አልነገርኩትም። እማዬ ከዚህ በኋላ ህክምና የሚፈይድላት ነገር ስለሌለ ወደቤቷ ወስደናት ዓይን ዓይኗን እያየሁ የምትሞትበትን ቀን መጠበቅ ትኩስ ቁስል ላይ ሚጥሚጣ እንደመበተን እየለበለበኝ እንደሆነ አልነገርኩትም። እቅፉ ውስጥ ሆኜ እዬዬ ብዬ ማልቀስ እንደምፈልግም። ከሰሞኑ አባቴን ሆስፒታል በማድረስ ሰበብ አዘውትረው ሲመጡ እህቴና ባሏን ማየት ልቤን በደም ፈንታ ቅናት እንደሚያስረጨው አልነገርኩትም። በእኔና በእርሱ መሃል ምንም ነገር እንደሌለ የሚሆነው መሆን እየከፋኝ አልቅሺ አልቅሺ እንደሚለኝ አልነገርኩትም። በዚህ ሁሉ ማጥ ውስጥ አቅፎኝ ያደረ ቀን የማግኩት ጠረኑን እርሱ አጠገቤ ሳይኖር እንኳን ካለበት ንፋሱ እያንጓለለ ለአፍንጫዬ እንደሚያቀብለው አልነገርኩትም። አጠገቤ ሆኖ ስለስራ እያወራኝ ልነካው እንደምፈልግ፣ ልስመው እንደምጎመዥ፣ እርሱ የኔ ቢሆንና በፈለግኩት ቁልምጫ ልጠራው እንደምመኝ… … አልነገርኩትም።]
“ማንናቸው?” አለኝ ዓይኔን ተከትሎ መኪና ውስጥ ያሉትን እህቴንና ባሏን እያያቸው
“እህምም…… እህቴ ናት! ባሏ ነው። አባቴን ወደቤት ሊያደርሱት እየጠበቁት ነው።” አልኩት አንገቴን ሰብሬ
“ታዲያ ምን?” አለኝ ዓይኔን እየፈለገ
“ምን?”
“ለምንድነው ስታያቸው በነበረው እይታ የምታያቸው? ምንድነው እሱ?”
“ኸረ ምንም አይደለም። በቃ ከእህቴ ጋር ስለማንነጋገር ነው።”
“አይደለም ራሁ። እያየሁሽ እኮ ነው። ቆይ ምንባደርግ ነው የተሰማሽን ልትነግሪኝ የምታምኚኝ? የበለጠ የቀረብኩሽ በመሰለኝ ቁጥር ለአካልሽ እንጂ ለልብሽ አልቀርብሽም። አብሬሽ ውዬ ባድር ቅርበቴ አይሰማሽም።…”
“ፍቅረኛዬ ነበረ። እህቴ ያገባችው ሰው…” ወቀሳውን እንዲያቆምልኝ ይሆን ለልቤ መቅረቡን እንዲያውቅልኝ አላውቅም። ነገርኩት!!
[ ዘጠነኛ ክፍል ስገባ አንድ ወንበር ላይ ከተቀመጥን ጀምሮ ብቸኛ ጓደኛዬ ዓለማየሁ እንደነበረ ግን አልነገርኩትም። የአስረኛ ክፍል ፈተና ተፈትነን ከተማሪዎች ጋር ከከተማ የወጣን ጊዜ ከንፈሬን ሲስመኝ ከርሱ ውጪ ያለውን ዓለም እንደረሳሁ አልነገርኩትም። በመከራ ከተከበበው ኑሮዬ የተረፈኝን ሰዓት ከርሱ ጋር ማሳለፌ በነገ ተስፋ እንዳልቆርጥ መፅናኛዬ ሆኖ በጥሩ ውጤት አብረን ዩንቨርስቲ እንደገባን አልነገርኩትም። ብዙ ጊዜ ‘ድብቅ ነሽ አላውቅሽም’ እያለ ቢነጫነጭም ይተወኛል ብዬ ለአፍታ አስቤ ባለማወቄ ሲተወኝ ከእማዬጋ አብሬ ማበድ ዳድቶኝ እንደነበረም አልነገርኩትም። የባሰው ደግሞ ከዓመታት በኋላ እሱ ዩንቨርስቲ አስተማሪ ሆኖ ተማሪው ከሆነችው እህቴ ጋር በአጋጣሚ ይሁን አስቦበት እስከአሁንም በማይገባኝ ሁናቴ ግንኙነት መጀመራቸውን ሆነ ብሎ ደውሎ የነገረኝ ማታ ራሴን ልስት እንደነበረ አልነገርኩትም። እህቴ ከዩንቨርስቲ በተባረረች በወራት ውስጥ የሰርጋቸው ጥሪ ካርድ ሲደርሰኝ ራሴን ባለመፈለግ ስሜት ውስጥ አዝቅጬው መብሰክሰኬን አልነገርኩትም። ከዓለማየሁ በፊትም በኋላም ሌላ ፍቅር እንደማላውቅም አልነገርኩትም።]
“እና አሁንም ድረስ ትወጂዋለሽ? እየቀናሽ ነው?” አለኝ
“አይይይ ለሱ ምንም ስሜት የለኝም። በሱ አልቀናም።”
“በሷ?” እያለኝ በጣም ተጠጋኝ። ትንፋሹ ጉንጮቼ ላይ እያቃጠለኝ አስቤ የተሰደሩ ቃላት መናገር አልችልም ነበር። በጭንቅላቴ ንቅናቄ ‘አዎን’ አልኩት። አልበቃውም እንድቀጥልለት ይጠብቃል። ምራቄ እያነቀኝ ነው።
“አባቴ ከእኔ እሷን ነበር የመረጠው። ፍቅረኛዬም… …” አላስጨረሰኝም ከንፈሬን በከንፈሩ ከደነው። መሳሙ ቀለምም ነበረው፣ ሽታም ነበረው፣ ጣዕምም ነበረው……
“በሚፈጠሩ ክስተቶች ውስጥ ራስሽን እየከተትሽ አትስፈሪ። ሁኔታዎች ሁሉ አንቺን ሚዛን ላይ አስቀምጠው አይለኩም።” አለኝ ለምን ያህል ደቂቃ እንደሆነ ስሞኝ ሲያበቃ… … ሰምቼዋለሁ? ገብቶኛልስ? መሳሙን እያጣጣምኩ ነበር።
“ተያቸው! እርሻቸው!” አለኝ ወደእነእህቴ እያየ። እያየኋቸው ነበር። የልጅ ስሜት ቢመስልም አዎን ሲስመኝ ማየታቸውን ለማረጋገጥ ነበር የማያቸው። አለ አይደለ እኔም ሰው አለኝ አይነት! አልጎዳችሁኝም አይነት! እንዳዩኝ በማወቄም በከፊል የታባታችሁ አይነት ስሜት……
በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ብዙ ነገር ተቀየረ። እንደውም ሁሉም ነገር!! እማዬ ወደቤት መጣች። ካስዬና አባቴ እቤታችን እየመጡ እናቴን መጠየቅ ጀመሩ። እኔና ፍትህ ቤተሰቦቻችን እስኪያውቁ እንደፍቅረኛሞች ገብተን መውጣት ጀመርን። ፍትህ የትዝታን ጉዳይ ተለዋጭ ቀጠሮ ሊጠይቅ በተዘጋጀበት ወቅት እጅ ያሰጠው ሁናቴ ተፈጠረ። አባቴ ሞቶ ተገኘ።
ቆይ ቆይ ፍትህ በትዝታ ጉዳይ ተስፋ መቁረጡ እና 25 ዓመት ሲፈረድባት መዋጡ ቀላል አልነበረም። ቤተሰቡን በሙሉ ያስከፈለ መስዋዕትነት እንጂ… …… ካልንበት እንቀጥል። አባቴ ተገደለ! ይቅርታ እንዳደርግለት ሲለማመጠኝ የነበረው አባቴ አንድስ እንኳን በጎ ቃል ሳልነግረው ሞተ። በራሴው ጉዳይ እርሱ አንዲት ጠጠር ባላበረከተበት የነገር ካብ ህይወቱን አጣ!! ለፍትህ ይሄ የመጀመሪያው መሆኑ እና ካላረፈ ሌሎቻችንም ተራ ጠባቂዎች መሆናችን እና ቀጣይዋ እኔ መሆኔ ማስጠንቀቂያ ደረሰው። ይሄኔ ነው እጅ የሰጠው! ከእኔ በላይ ሁሉ የተጎዳ መሰለኝ።
“በፍፁም አንቺን ለምርጫ ማቅረብ አልችልም። አንቺን ማጣት አልችልም።” ይለኛል እየደጋገመ። ለማን እንዳለቀሰ ያልገባኝን ለቅሶ በአባቴ ቀብር ላይ ምርር ብሎ አለቀሰ። ግራ የገባው ስሜት ውስጥ ጠለቅኩ። አንዱ አካሌ ሽባ የሆነ ነገር ይመስለኛል። ከሬሳው ጋር የቀበርኩት ነገር ያለ ይመስል የሆነ ስሜቴ ወደአባቴ መቃብር ይጎትተኛል።
የባሰው ነገር ለእናቴ የፍቅሯን ሞት ማርዳት ነበር። በየቀኑ እየመጣ ሲያያት የከረመውን ሰው በምንም ሰበብ ቀረ ልንላት አንችልም። እንደገና እንደተዋት በምንም ምክንያት ሰንገን ብንነግራት ጤነኛ አትሆንም። መሞቱንም ብታውቅ ጤነኛ አትሆንም። ቢያንስ ግን ከመከዳት ስሜት ፍቅረኛዋ እያፈቀራት መሞቱን ማወቋ ይሻላል በሚል ተስማምተን የተሻለ ሁኔታ ላይ ያለው ካስዬ ነገራት። ዝም አለች። ለሁለት ሰዓታት ዝም አለች። እኔን የምታይበትን መንገድ አልወደድኩትም። ያንቺ ጦስ ነው ፍቅሬን ያሳጣኝ አይነት መልዕክት አለው። ድንገት ከየት ባመጣችው ጉልበት እንደሆነ እንጃ ተስፈንጥራ ተነስታ ቀብሩን እሄዳለሁ ብላ አመሰችን። ካስሽ ይዟት ሄደ። ካስሽ ደግፏት ፍቅሯ አፈር ሲገባ አነባች። አለቃቀሷ ግጥምም ቃልም ሳይኖረው ዜማ አለው። እያየኋት ለአባቴ ይሁን ለእርሷ ብቻ አነባሁ! ስለእውነት የውብዳር እንኳን ስታለቅስ አሳዘነችኝ። በየመሃሉ ለሞቱ ተጠያቂ መሆኔን ልትነግረኝ አንዳንድ ሀረግ ትመዛለች። እህቴ አፈሩ ላይ ተልሞሰሞሰች። ትንፋሽ አጥሮኝ ደረቴ ላይ ሲያፍነኝ ነው ቀብሩ ያበቃው እና ወደቤታችን የተመለስነው።
እቤት ከመግባታችን እማዬ “ይሄ የበረራ ቁጥር… …” ማለት ጀመረች። መሬቷ ያንሳፈፈችኝ አይነት ስሜት ተሰማኝ። ግራቪቲ የከዳኝ! ያልበላሁት ምግብ ወደ ላይ ወደላይ አለኝ። እሪሪሪ ብዬ ማልቀስ እፈልጋለሁ። ግን ጉሮሮዬም ደረቴም የታፈነ ይመስለኛል።
“እኔ አለሁ አንቺ እረፊ!” አለኝ ካስዬ። እንዳለውም ከዚያን ቀን በኋላ ኖረ። ምክንያቱም በሚቀጥሉት ቀናት እናቴ ማነሽ? ማለት ጀመረች። ፍትህንም ስታይ መበርገግ ጀመረች። የሚገርመው ካስዬን በባሏ ስም አንድዬ
👍8❤1😁1
እያለች መጥራት ጀመረች። ከእርሱ ውጪ ማንንም አታስጠጋም። (ሀኪሟ እሷ እንኳን ሳታውቀው ለካስዬ የሆነ የተለየ ስሜት እንደነበራት እና ሲያማት ከፍቅሯ ጋር እንደተማታባት ሳይኮሎጂ ጠቅሶ መላ ምት መታ።) ፍትህ በኔ ልመናና ጭቅጨቃ ይግባኝ በመጠየቁ ስጋቱ ሊያሳብደው ደርሶ ራቅ ያለ ቦታ አዲስ ቤት ተከራይተን አብረን መኖር ጀመርን።
” 20 ዓመት ሙሉ ያላየሁት አባቴ ለወራት ካጠገቤ ነበረ። ይቅር በይኝ እያለኝ ፣ እንደምጠላው እያሰበ… አልጠላህም ሳልለው፣ ስናፍቅህ ነው የኖርኩት ሳልለው፣ ይቅር ብዬሃለሁ ሳልለው ነው የገደሉት……” እንባዬን ማስቆም ተስኖኝ በመሃከላችን ባለው ርቀት እንዲሰማት ጮክ እያልኩ ለትዝታ ነው የምነግራት። አትመልስልኝም። የአባቴ መሞትም የእኔ እንባም ስሜት የሰጣት አትመስልም።
“እናቴ ልትሞትብኝ ነው። በሰዎችሽ ጦስ አዕምሮዋ ተቃውሶ እኔን ልጇን እንኳን አታውቀኝም። ያ ምን ማለት እንደሆነ ታውቂያለሽ? ማን እንደሆንኩ ሳታውቅ ሳትሰናበተኝ እማዬ ትሞትብኛለች ማለት ነው።” ብዙ የሀሳብ ድሮች ያደሩበት በሚመስል ጠባብ እይታ ታየኛለች እንጂ አትመልስልኝም።
“ፍቅረኛሽን አስገድለውታል። አንቺንም ለማይሆን ህይወት ዳርገውሻል። ሀያ አምስት ዓመት ወህኒ እንድትበሰብሺ አጨብጭበው ሸኝተውሻል።ልጅሽም ነገ እጣዋ ምን እንደሆነ አይታወቅም። እና አሁንም ለእነርሱ ትከራከሪያለሽ! ምንድነው ችግርሽ? አሁን ካለሽበት የባሰ ምን እንዳይመጣ ነው?…… ” ለፍልፌ ሳበቃ
“እወደዋለሁ።” አለችኝ
“ማንን?” የማስበው እውነት ባይሆንና ብንንን ብሎ ቢጠፋ እየተመኘሁ
“ሰለሞንን!”(አጎቷ ነው) ደነዘዝኩ። ከሁለት አንዳችን ጤነኛ ባንሆን ነው። ለተከታዮቹ ደቂቃዎች እሷ ተናጋሪ እኔ በድን ሰሚ ሆንን። ትቻት ስወጣም በድኔን እየጎተትኩ ነበር። ጭንቅላቴ ውስጥ የሀሳብ መዘውር ያለ ይመስለኛል። አንዱ ሀሳብ ሌላውን እያስከተለ በመዘውሩ የሚፈጭ…… ርርርርር የሚል የሞተር ድምፅ ያለው መዘውር።
ሰውየው አስገድዷት አይደለም። ገና ከ12 አመቷ ጀምሮ እያባበለ ያስለመዳት የስድ ጨዋታ ነው። ለምዳዋለች። ልምዱን አልጠላችውም። እንደውም ስታወራኝ እንኳን ከሚወዱት ፍቅረኛ ጋር እንዳሳለፉት ጣፋጭ ጊዜ የፊቷ ፀዳል እየበራ ነው። በመጀመሪያ ፊልሞች ያሳያታል። እያንገላቱ፣ እያሰቃዩና እየገረፉ የሚረኩ ወንዶች ፊልም… … በስቃዩ ውስጥ የተሳመች ያህል በማቃሰት የምታብድ… … እንዲያሰቃያት የምትለምን ሴት ያለችበት ፊልም… … ቀስ በቀስ አለማመዳት። ጤነኛ ሰው ሊወደው የማይችለውን sex torture እንደ ሱስ ለመደችው። ደስ ብሏትና ፈልጋ የምታደርገው ቅውሰት ሆነ። አጎትየውን ከሴት ጋር ስላገኘችው በእልህ ታዲዎስን ፍቅረኛዋ አደረገችው። ሰላማዊው ታዲዎስ አጎቷ የሚነዳትን የእብደት ቁልቁለት ሊያንቆለቁላት አይችልምና ሱስ እንዳባዘተው ወመኔ በሱስ ጥም አዛጋች። ከሁለቱም ጋር ሆነች። በዚህ መሃል የአጎቷን ልጅ አረገዘች። ታዲዎስ የእኔ ልጅ ነው ብሎ ቁምስቅሏን ሲያሳያት ነው እውነቱን የነገረችውና የዘመኑ ቁጥር በአጎቷ በጎ ፈቃደኝነት እንዲወሰን የፈረደችበት። ከዛ የቫንፓየር ወይ የማርስ ፍጡሮች ተረት እንጂ ሰውነት የማይመስል አኗኗር ሰውየው ከወንድሙ ልጅጋር እንደባልና ሚስት ኖሩ።… … የዛን ዕለት ምሽት ሴት ይዞ እቤት መጣ! በቅናት የነደደ አካሏ ያዘዛትን አደረገች። ምንም የማታውቅ ንፁህ ነፍስ ጠፋች።
“ልጄ ከአጎቴ እንደወለድኳት እንድታውቅ አልፈልግም። ሶልም ይሄ ነገሩ ቢታወቅ ስሙ ይጠፋል፣ ይታሰራል። የወንድሙም ስም አብሮ ይነሳል(ባለስልጣን ወንድሙን ማለቷ ነው።) ሶልን እወደዋለሁ። መጥፎ ነገር እንዲደርስበት አልፈልግም።” አለችኝ የሆነ ልክ የሆነ ነገር እንደነገረችኝ ሁሉ ሀፍረት ሳይሰማት። ዘገነነችኝ። በእርግጥ አሳዘነችኝም። የሆነ አይነት በሽታ እንደሚሆን አሰብኩ። የገዛ ሰውነቴ እየሸከከኝ ወጣሁ። ጭንቅላቴ ውስጥ ያለው መዘውር አልቆመም።
የኑሯችን መዘውር የሚዞረው በሚገጥሙን ክስተቶች ግብዓትነት አይደለም እያልኩ አስባለሁ። ይልቅስ በገጠሙን ክስተቶች ላይ በወሰንነው ውሳኔና በዘረጋነው እርምጃ እንጂ…… ኑሯችን የውሳኔያችን ውጤት እንጂ ያጋጠሙን መከራና ፍሰሃ ውጤት አይደለም። ……
“ literally she is sick, serious ህክምና ያስፈልጋታል።” አለኝ ፍትህ ነገሩን ስነግረው እየሰቀጠጠው።
“ከአሁን በኋላ የትዝታ ኬዝ አይደለም። አባቷን በስድ ግፈኞች የተቀማች ልጅ ኬዝ ነው። የራሴ ጉዳይ ነው።” አልኩኝ ከመናገሬ በፊት ያሰብኩት ያልመሰለኝን ንግግር!
🌑አለቀ🌑
ታሪኩን በመከታተል አስተያየታችሁን ላደረሳችሁን በሙሉ እናመሰግናለን🙏
አስተያየት ካሎ በ @atronosebot አድርሱን
አስተያየት መስጠት ላልተመቻችሁ Like👍 በማድረግ አብሮነታችሁን አሳዩን።
” 20 ዓመት ሙሉ ያላየሁት አባቴ ለወራት ካጠገቤ ነበረ። ይቅር በይኝ እያለኝ ፣ እንደምጠላው እያሰበ… አልጠላህም ሳልለው፣ ስናፍቅህ ነው የኖርኩት ሳልለው፣ ይቅር ብዬሃለሁ ሳልለው ነው የገደሉት……” እንባዬን ማስቆም ተስኖኝ በመሃከላችን ባለው ርቀት እንዲሰማት ጮክ እያልኩ ለትዝታ ነው የምነግራት። አትመልስልኝም። የአባቴ መሞትም የእኔ እንባም ስሜት የሰጣት አትመስልም።
“እናቴ ልትሞትብኝ ነው። በሰዎችሽ ጦስ አዕምሮዋ ተቃውሶ እኔን ልጇን እንኳን አታውቀኝም። ያ ምን ማለት እንደሆነ ታውቂያለሽ? ማን እንደሆንኩ ሳታውቅ ሳትሰናበተኝ እማዬ ትሞትብኛለች ማለት ነው።” ብዙ የሀሳብ ድሮች ያደሩበት በሚመስል ጠባብ እይታ ታየኛለች እንጂ አትመልስልኝም።
“ፍቅረኛሽን አስገድለውታል። አንቺንም ለማይሆን ህይወት ዳርገውሻል። ሀያ አምስት ዓመት ወህኒ እንድትበሰብሺ አጨብጭበው ሸኝተውሻል።ልጅሽም ነገ እጣዋ ምን እንደሆነ አይታወቅም። እና አሁንም ለእነርሱ ትከራከሪያለሽ! ምንድነው ችግርሽ? አሁን ካለሽበት የባሰ ምን እንዳይመጣ ነው?…… ” ለፍልፌ ሳበቃ
“እወደዋለሁ።” አለችኝ
“ማንን?” የማስበው እውነት ባይሆንና ብንንን ብሎ ቢጠፋ እየተመኘሁ
“ሰለሞንን!”(አጎቷ ነው) ደነዘዝኩ። ከሁለት አንዳችን ጤነኛ ባንሆን ነው። ለተከታዮቹ ደቂቃዎች እሷ ተናጋሪ እኔ በድን ሰሚ ሆንን። ትቻት ስወጣም በድኔን እየጎተትኩ ነበር። ጭንቅላቴ ውስጥ የሀሳብ መዘውር ያለ ይመስለኛል። አንዱ ሀሳብ ሌላውን እያስከተለ በመዘውሩ የሚፈጭ…… ርርርርር የሚል የሞተር ድምፅ ያለው መዘውር።
ሰውየው አስገድዷት አይደለም። ገና ከ12 አመቷ ጀምሮ እያባበለ ያስለመዳት የስድ ጨዋታ ነው። ለምዳዋለች። ልምዱን አልጠላችውም። እንደውም ስታወራኝ እንኳን ከሚወዱት ፍቅረኛ ጋር እንዳሳለፉት ጣፋጭ ጊዜ የፊቷ ፀዳል እየበራ ነው። በመጀመሪያ ፊልሞች ያሳያታል። እያንገላቱ፣ እያሰቃዩና እየገረፉ የሚረኩ ወንዶች ፊልም… … በስቃዩ ውስጥ የተሳመች ያህል በማቃሰት የምታብድ… … እንዲያሰቃያት የምትለምን ሴት ያለችበት ፊልም… … ቀስ በቀስ አለማመዳት። ጤነኛ ሰው ሊወደው የማይችለውን sex torture እንደ ሱስ ለመደችው። ደስ ብሏትና ፈልጋ የምታደርገው ቅውሰት ሆነ። አጎትየውን ከሴት ጋር ስላገኘችው በእልህ ታዲዎስን ፍቅረኛዋ አደረገችው። ሰላማዊው ታዲዎስ አጎቷ የሚነዳትን የእብደት ቁልቁለት ሊያንቆለቁላት አይችልምና ሱስ እንዳባዘተው ወመኔ በሱስ ጥም አዛጋች። ከሁለቱም ጋር ሆነች። በዚህ መሃል የአጎቷን ልጅ አረገዘች። ታዲዎስ የእኔ ልጅ ነው ብሎ ቁምስቅሏን ሲያሳያት ነው እውነቱን የነገረችውና የዘመኑ ቁጥር በአጎቷ በጎ ፈቃደኝነት እንዲወሰን የፈረደችበት። ከዛ የቫንፓየር ወይ የማርስ ፍጡሮች ተረት እንጂ ሰውነት የማይመስል አኗኗር ሰውየው ከወንድሙ ልጅጋር እንደባልና ሚስት ኖሩ።… … የዛን ዕለት ምሽት ሴት ይዞ እቤት መጣ! በቅናት የነደደ አካሏ ያዘዛትን አደረገች። ምንም የማታውቅ ንፁህ ነፍስ ጠፋች።
“ልጄ ከአጎቴ እንደወለድኳት እንድታውቅ አልፈልግም። ሶልም ይሄ ነገሩ ቢታወቅ ስሙ ይጠፋል፣ ይታሰራል። የወንድሙም ስም አብሮ ይነሳል(ባለስልጣን ወንድሙን ማለቷ ነው።) ሶልን እወደዋለሁ። መጥፎ ነገር እንዲደርስበት አልፈልግም።” አለችኝ የሆነ ልክ የሆነ ነገር እንደነገረችኝ ሁሉ ሀፍረት ሳይሰማት። ዘገነነችኝ። በእርግጥ አሳዘነችኝም። የሆነ አይነት በሽታ እንደሚሆን አሰብኩ። የገዛ ሰውነቴ እየሸከከኝ ወጣሁ። ጭንቅላቴ ውስጥ ያለው መዘውር አልቆመም።
የኑሯችን መዘውር የሚዞረው በሚገጥሙን ክስተቶች ግብዓትነት አይደለም እያልኩ አስባለሁ። ይልቅስ በገጠሙን ክስተቶች ላይ በወሰንነው ውሳኔና በዘረጋነው እርምጃ እንጂ…… ኑሯችን የውሳኔያችን ውጤት እንጂ ያጋጠሙን መከራና ፍሰሃ ውጤት አይደለም። ……
“ literally she is sick, serious ህክምና ያስፈልጋታል።” አለኝ ፍትህ ነገሩን ስነግረው እየሰቀጠጠው።
“ከአሁን በኋላ የትዝታ ኬዝ አይደለም። አባቷን በስድ ግፈኞች የተቀማች ልጅ ኬዝ ነው። የራሴ ጉዳይ ነው።” አልኩኝ ከመናገሬ በፊት ያሰብኩት ያልመሰለኝን ንግግር!
🌑አለቀ🌑
ታሪኩን በመከታተል አስተያየታችሁን ላደረሳችሁን በሙሉ እናመሰግናለን🙏
አስተያየት ካሎ በ @atronosebot አድርሱን
አስተያየት መስጠት ላልተመቻችሁ Like👍 በማድረግ አብሮነታችሁን አሳዩን።
👍11
#ስኳር_መች_ይጣፍጣል?!
በዚህ እጅ ያልነካው ወዳጅ በማይገኝበት ክፉ ዘመን ሰላሳ አራት አመት እስኪሞላት ድረስ የማንም እጅ ሳይነካካት ከወር በፊት የተሞሸረች ልጃገረድ ወዳጅ አለችኝ።
‹‹ያላገባኝ አይነካኝም!›› ብላ….
‹‹ወንድ ልጅ ወተቱን በነፃ ካገኘ ላሚቱን አይገዛም›› ብላ…
ስንቱን የወንድ ፈንጂ በጥንቃቄ እንጣጥ ብላ፣ ስንቱን አማላይና አታላይ አምልጣ፣ እሷም እንደማንም ግጣሟን አገኘችና ጎጆ ወጣች። ተሰበሰበች። አገባች….ተነካች።
በቃል እና በእምነቷ መሰረት፣ ክብር እና ንፅህንናዋን ጠብቃ ኖረ ተዳረች። ከባሏ ተኛች።
በዚህ ዘመን ቀረ ብለን የምንገረምበት ወግ አጥባቂነቷ የአስናቀች ወርቁን ዘፈን ያስታውሰኝ ነበር። አስናቀች ቀኑን ሙሉ ከምታፈቅረው ልጅ ውላ ልክ ሲመሽ ሌላ እንዳያስብ ‹‹ልሂድ›› ስለምትል ወዳጄን የምትመስል ሴት ዘፍናልን ነበር።
‹‹ፍቅርዬ- ፍቅርዬ ደህና ሁን
ሊመሽ ስለሆነ መሄዴ ነው አሁን…..
…እኔ እንደምወድህ – ፍቅሬ ሆይ ውደደኝ
በህጋዊ ስርአት ማልድና ውሰደኝ…
አፍቅረኝ ላፍቅርህ ኑሯችን ባንድ ይሁን
እስከዚያው ድረስ ግን- ፍቅርዬ ደህና ሁን›› እያለች ዘፍናልን ነበር።
እናም…የ34 አመቷ ወዳጄም በህጋዊ ስርአት፣ በአማላጅና በምልጃ የፈለገችውና የፈለገችውን አገኘችና፣ ወሰዳትና አገባች። ተነካች።
ሰርጉ ተከናውኖ…
ጫጉላው አብቦ…
ከስንት ያመለጠው ብር አምባር ተሰብሮ ጥቂት ቀናት ካለፉ በኋላ አሁንስ ይበቃታል ብዬ ደወልኩላት። እንዴት ሆንሽ….አጥሚትና ገንፎ የት ይዘን እንምጣ ልል እና ላጫውታት ደወልኩላት።
ብዙ ሳይጠራ አነሳች።
(በቅቷታል ማለት ነው…)
ሰላምታችን ሲያልቅ ወደ አንገብጋቢውጉዳይ ገባሁና..
‹‹እህስ…ነገሩስ? እንደጠበቅሸው አገኘሽው ወይስ ቅር አለሽ?›› አልኳት።
‹‹ቅር አለሽ ወይ? ወይ ጉድ…አንቺ….ስኳር መች ይጣፍጣል?!›› ብላ መለሰችልኝ።
ከአንጀቴ ሳቅሁ።
እንዲህ ትላለች ብዬ ስላልጠበቅኩም፣ ያ ከአመታት በፊት የሰማሁት ታሪክ ላይ ያለችው ልጅንም አስታወሰችኝና ሳቅሁ።
(ታሪኩ እንዲህ ነው። ልጅቱ ለስኳር ያላት ፍቅር የትዬሌሌ ነው። ‹‹ከስኳር የሚጥም፣ ከስኳር የሚጣፍጥ ነገር በአለም ላይ…አንዳችም ነገር የለም›› የምትል አይነት። እጮኛዋ ‹‹ተይ ተጋብተን ፍቅር ስንሰራ ኋላ ሃሳብሽን ትለውጫለሽ›› ቢላትም እሷ ግን ወይ ፍንክች! በኋላ ጋብቻው ተከናውኖ ባልና ሚስት ለመጀመሪያ ጊዜ ፍቅር እየሰሩ ወደ ማገባደዱ ሲደርሱ የሚስቱን ሁኔታ ያየው ባል በእጁ የጨበጠውን ስኳር በተከፈተ አፏ ውስጥ ሙጅር ያደርጋል። ይሄን ጊዜ የስኳር ነገር የማይሆንላት ሚስቱ ምን አለች? ‹‹ውይ ውዴ…! የምን አፈር ነው አፌ ውስጥ የጨመርከው?!››)
‹‹ወይ አንቺ…እና ታዲያ ይሄን ያህል ጊዜ በመቆየትሽ ትንሽ አልተቆጨሽም ታዲያ?›› አልኳት
ለመመለስ ሰከንድ አልፈጀባትም።
‹‹በጭራሽ! መቆየቴ መቼም አይቆጨኝም….ግን እንዲህ መሆኑን ግን ነገራችሁኝ አታውቁም….››
‹‹ ብንነግርሽስ ኖሮ?››
‹‹እሱስ ምንም ለውጥ አያመጣም ነበር…ያው ምናልባት ትንሽ…ይበልጥ ልጓጓ ግን እችል ነበር……..››
ወሬያችን አልቆ ስልኩን ስዘጋ በዚህ ሁሉም ሰው ሁሉንም ሰው ለመምሰል በሚሮጥበት ጊዜ፣ ለግል አቋምና እምነቷ ባላት ታማኝነት እንዳዲስ ተደነቅኩባት። ቀናሁባት።
ከዚህ ሁሉ በላይ ግን (በእኔ እና በአለም ስሌት) ዘግይታም ቢሆን አዳሜ የአለምን ምሬት የሚያጣፍጠው ፍቅርን በመስራት ስኳር መሆኑን በማወቋ ተደሰትኩላት።
🔘በሕይወት እምሻው🔘
በዚህ እጅ ያልነካው ወዳጅ በማይገኝበት ክፉ ዘመን ሰላሳ አራት አመት እስኪሞላት ድረስ የማንም እጅ ሳይነካካት ከወር በፊት የተሞሸረች ልጃገረድ ወዳጅ አለችኝ።
‹‹ያላገባኝ አይነካኝም!›› ብላ….
‹‹ወንድ ልጅ ወተቱን በነፃ ካገኘ ላሚቱን አይገዛም›› ብላ…
ስንቱን የወንድ ፈንጂ በጥንቃቄ እንጣጥ ብላ፣ ስንቱን አማላይና አታላይ አምልጣ፣ እሷም እንደማንም ግጣሟን አገኘችና ጎጆ ወጣች። ተሰበሰበች። አገባች….ተነካች።
በቃል እና በእምነቷ መሰረት፣ ክብር እና ንፅህንናዋን ጠብቃ ኖረ ተዳረች። ከባሏ ተኛች።
በዚህ ዘመን ቀረ ብለን የምንገረምበት ወግ አጥባቂነቷ የአስናቀች ወርቁን ዘፈን ያስታውሰኝ ነበር። አስናቀች ቀኑን ሙሉ ከምታፈቅረው ልጅ ውላ ልክ ሲመሽ ሌላ እንዳያስብ ‹‹ልሂድ›› ስለምትል ወዳጄን የምትመስል ሴት ዘፍናልን ነበር።
‹‹ፍቅርዬ- ፍቅርዬ ደህና ሁን
ሊመሽ ስለሆነ መሄዴ ነው አሁን…..
…እኔ እንደምወድህ – ፍቅሬ ሆይ ውደደኝ
በህጋዊ ስርአት ማልድና ውሰደኝ…
አፍቅረኝ ላፍቅርህ ኑሯችን ባንድ ይሁን
እስከዚያው ድረስ ግን- ፍቅርዬ ደህና ሁን›› እያለች ዘፍናልን ነበር።
እናም…የ34 አመቷ ወዳጄም በህጋዊ ስርአት፣ በአማላጅና በምልጃ የፈለገችውና የፈለገችውን አገኘችና፣ ወሰዳትና አገባች። ተነካች።
ሰርጉ ተከናውኖ…
ጫጉላው አብቦ…
ከስንት ያመለጠው ብር አምባር ተሰብሮ ጥቂት ቀናት ካለፉ በኋላ አሁንስ ይበቃታል ብዬ ደወልኩላት። እንዴት ሆንሽ….አጥሚትና ገንፎ የት ይዘን እንምጣ ልል እና ላጫውታት ደወልኩላት።
ብዙ ሳይጠራ አነሳች።
(በቅቷታል ማለት ነው…)
ሰላምታችን ሲያልቅ ወደ አንገብጋቢውጉዳይ ገባሁና..
‹‹እህስ…ነገሩስ? እንደጠበቅሸው አገኘሽው ወይስ ቅር አለሽ?›› አልኳት።
‹‹ቅር አለሽ ወይ? ወይ ጉድ…አንቺ….ስኳር መች ይጣፍጣል?!›› ብላ መለሰችልኝ።
ከአንጀቴ ሳቅሁ።
እንዲህ ትላለች ብዬ ስላልጠበቅኩም፣ ያ ከአመታት በፊት የሰማሁት ታሪክ ላይ ያለችው ልጅንም አስታወሰችኝና ሳቅሁ።
(ታሪኩ እንዲህ ነው። ልጅቱ ለስኳር ያላት ፍቅር የትዬሌሌ ነው። ‹‹ከስኳር የሚጥም፣ ከስኳር የሚጣፍጥ ነገር በአለም ላይ…አንዳችም ነገር የለም›› የምትል አይነት። እጮኛዋ ‹‹ተይ ተጋብተን ፍቅር ስንሰራ ኋላ ሃሳብሽን ትለውጫለሽ›› ቢላትም እሷ ግን ወይ ፍንክች! በኋላ ጋብቻው ተከናውኖ ባልና ሚስት ለመጀመሪያ ጊዜ ፍቅር እየሰሩ ወደ ማገባደዱ ሲደርሱ የሚስቱን ሁኔታ ያየው ባል በእጁ የጨበጠውን ስኳር በተከፈተ አፏ ውስጥ ሙጅር ያደርጋል። ይሄን ጊዜ የስኳር ነገር የማይሆንላት ሚስቱ ምን አለች? ‹‹ውይ ውዴ…! የምን አፈር ነው አፌ ውስጥ የጨመርከው?!››)
‹‹ወይ አንቺ…እና ታዲያ ይሄን ያህል ጊዜ በመቆየትሽ ትንሽ አልተቆጨሽም ታዲያ?›› አልኳት
ለመመለስ ሰከንድ አልፈጀባትም።
‹‹በጭራሽ! መቆየቴ መቼም አይቆጨኝም….ግን እንዲህ መሆኑን ግን ነገራችሁኝ አታውቁም….››
‹‹ ብንነግርሽስ ኖሮ?››
‹‹እሱስ ምንም ለውጥ አያመጣም ነበር…ያው ምናልባት ትንሽ…ይበልጥ ልጓጓ ግን እችል ነበር……..››
ወሬያችን አልቆ ስልኩን ስዘጋ በዚህ ሁሉም ሰው ሁሉንም ሰው ለመምሰል በሚሮጥበት ጊዜ፣ ለግል አቋምና እምነቷ ባላት ታማኝነት እንዳዲስ ተደነቅኩባት። ቀናሁባት።
ከዚህ ሁሉ በላይ ግን (በእኔ እና በአለም ስሌት) ዘግይታም ቢሆን አዳሜ የአለምን ምሬት የሚያጣፍጠው ፍቅርን በመስራት ስኳር መሆኑን በማወቋ ተደሰትኩላት።
🔘በሕይወት እምሻው🔘
👍5
#ማፍቀር_ወይስ_መለየት ?
:
#አጭር_ልብወለድ
:
ቅዳሜ ከሰአት በኋላ ፣ፀጥ ረጭ ብሏል፣ የቤታችን የግድግዳ ሰአት ብቻ . . .ችው . . . ችው
እያለ በዚህ ፀጥታ ውስጥ ይሰማል። ማንም የለም እኔና እኔ ብቻ። በውስጤ የብቸኝነት ስሜት ተሰማኝ። በዚህ በጠራራ ፀሐይ እቤት ውስጥ ለብቻ መቀመጥ ምን ያህል ይከብዳል እያልኩ ከራሴ ጋር አወራለው።
ዞር ብዬ ክላሲካል ሙዚቃ ሲያሰማ ወደ ነበረው ቴፕ ስመለከት መብራት ሄዶ ዝም እንዳለ ታወቀኝ። ሀሳቤን ሰበሰብኩና በእጄ ወደያዝኩት ልብ ወለድ መፅሀፍ አቀርቅሬ ማንበቤን ቀጠልኩ።
በጥሩ ተመስጦ ውስጥ እንዳለው ድንገት ከአጠገቤ የነበረው ስልክ ጮኸና ቀልቤን ገፈፈው።በጣም ደነገጥኩ። በራሴ መደንገጥ ተገረምኩና እራሴን አረጋግቼ የስልኩን እጀታ በጉጉት አነሳሁት።
<<ሃሎ>> አልኩኝ በትህትና
<<ሄሎ>> አለችኝ አንዲት ልጅ በሚያባባና በሚያምር የድምፅ ቅላፄ።
<<ማንን ፈለጉ ?>>
<<እ. . .ናሆምን ላገኘዉ እችላለሁ ?>>
በዚህን ግዜ የልብ ትርታዬ ፍጥነቱን ጨመረ።
ድምፆም አዲስና የሚማርክ ስለሆነብኝ ማን ልትሆን ትችላለች? በሚል ከራሴ ጋር ትንሽ ተሟገትኩና።
<<ነኝ. . . ማን ልበል?>>
<<. . . ሜሮን እባላለሁ >>
<<ሜሮን?.. .ይቅርታ. . . አላስታወስኩሽም፣ ሜሮን ማን ?>>
<<ሜሮን አለሙ>>
አሁንም ፈፅሞ ላስታውሳት አልቻልኩም።ሜሮን የምትባል ልጅ ፈፅሞ ማወቄን እርግጠኛ አልነበርኩም።
<<በ. .ጣም.. ይቅርታ የኔ እህት አላወኩሽም።>>
<<ይገርምሀል እኔም አላውቅህም።>>
<<የደወልሽው አንቺ መሰለሽኝ?>>
<<አልተሳሳትክም፤ ማለቴ ስልክህን የአስረኛ ክፍል ማስታወሻ ደብተሬ ላይ ከበስተጀርባው ተፅፎ ነው ያገኘሁት።ሁለት አመት እንዳለፈውና በራሴ እጅ ፅሁፍ ስለመፃፉ እርግጠኛ ነኝ ነገር ግን በምን ቀንና ሁኔታ እንደተፃፈ አላስታውሰውም
<<እና?>>
<<እናማ ብዙጊዜ ሲከነክነኝ የነበረ ስልክ ቁጥር ስለነበር ምን አልባት አንተ ካወከኝ በሚል ነበር የደወልኩት።
መልሶን ማመን አቃተኝ።ለሰኮንዶች ያህል በአይኔ የማውቃቸውን እንስቶች በአይነ ህሊናዬ እየቃኘኋቸው ድምፅን ከምስል ጋር ለማዛመድ ሞከረኩ።ሆኖም በፍፁም ልትመጣልኝ አልቻለችም ።በርግጥ ከሁለት አመት በፊት ስለተከሰተ ነገር ማስታወስ ይከብዳል።
የቀረን ነገር ቢኖር በግምት ልንተዋወቅበት የምንችልበትን ሁኔታ መመርመር ነውና ስለየግል ህይታችን መነጋገር ጀመርን።ስለ ት/ቤትና ስለመኖርያ ስፍራችን፣ ስለቤተሰብ እንዲሁም ስለ ቅርብ ጓደኞቻችን ሳይቀር በግልፅ ተወያየን።በሚገር ሁኔታ ግን አሁንም ከጥርጣሬ ያለፈ እዚህ ቦታ ይሆናል ብለን መወሰን ተቸገርን።
ለቀልድ ነው ብዬ እንኳን እንዳልጠረጥራት የምትሰጠኝ መልሶች ሁሉ ግልፅና ፈጣን ነበሩ።
በተለይ ከንግግሯ በራስ መተማመንና በሳልነቷን ለመገመት ይቻል ነበር።ሁኔታው ቢያስገርመኝም ቀስ በቀስ ምርመራውን ትተን ስለየጎል ህይወታችን ገብተነሰ መጨዋወት ጀመርን።
<<ምን አየሰራሽ ነው አሁን?>>
<<ያው አስረኛ ከጨረስኩ በኋላ የሁለት አመት አካውንቲንግ ፊልድ ተምሬ ነግል ድርጅት ውስጥ በመስራት ላይ ነኝ። አንተስ?>>
<<እኔ እንደምንም የመሰናዶ ትምህርት ተምሬ አ.አ.ዮ የአስተዳደር ትምህርት በመማር ላይ ነኝ>>
<<ኦው ጎበዝ ተማሪ ነሃ . . .!>>
<<ነኝ ብለሽ ነው . . . ለመሆኑ ግን ምን ከይነት ሰው ነሽ ማለቴ መልክሽን?>>
<<...እኔጃ ለመግለፅ ይከብዳል።>> ሳቅ እያለች።
<<ታድያ.... ለምን በአካል አንገናኝም፤ >>ምን አልባት በመልክ ልንተዋወቅ እንችላለን?
ጥያቄውን በድፍረት ነበር ያነሳሁት ፤ሆኖም በፍርሀቴ ልክ መልኳን ለማየት ጉጉቱ ነበረኝ። እርሷም በመግደርደር ይሁን አላውቅም።
<<..መገናኘቱ እንኳን የሚመች አይመስለኝም።>
<<ለምን?>>
<<እኔንጃ?>>
<<ፈራሽ እንዴ?>>
<<አይ መፍራት ሳይሆን ሰሞኑን ክፍት ሰአት ስለሌለኝ ነው።>>
ንግግሯ እንደማቅማማት አይነት ነበር ፤ እርግጠኛ አልነበረችም።
<<እሺ. . . ብዙ አላስጨንቅሽም ባይሆን ስልክሽን ስጭኝና ተደዋውለን ሌላ ግዜ እንገናኛለን።>>
ለተወሰኑ ሰኮንዶች ዝም አለች።የኔንም ግራ መጋባት ጥርጣሬ አጎላችው።
<<ምነው ዝም አልሽ?>>
<<...ስልክም አሁን ልሰጥክ አልችልም።>>
<<እህ..ያሁሉ የግል መረጃሽን በግልፅነት ስትነግሪኝ ቆይተሽ እንዴትስልክ መስጠት ከበደሽ?>>
<<በፍፁም መደበቄ አይደለም።በዚህን ሰአት እኔን የምታገኝበት ስልክ ምን አልባት ለሁለት ቀን ብቻ የሚቆይ ነው ። ሌላ ስልክ በሌላ ግዜ እንጂ አሁን ልሰጥክ አልችልም ወይም አላውቀውም።>>
<<አሀ ገባኝ፣ ቤት ልትቀይሩ ነው አይደል?>>
<<አረ አይደለም >>ሳቅ እያለች ነበር።
<<ምንድን ነው እሱ ግልፅ ሁኚ እንጂ የደበቅሽው ነገር ኦንዳለ ይሰማኛል።>>
<<በቃ ለምን ነገ ወደ ማታ አንገናኝም?>>
የአቋም ለዉጧ አስገርሞኛል፣አስደንግጦኛልም።
አሁን ለመናገር ያልፈለገችው ሚስጥሯም ከልብ አጓጓኝ።
<<ጥሩ የት እንገናኝ?>>
<<ፒያሳ ያለው ቤቲ ካፌ ይመችካል?>>
<<ደስ ይለኛል ስንት ሰአት?>>
<<አስራ ሁለት ሰአት።>>
የሰአት ምርጫዋ ወደ ማታ መሆኑ አይናፋርነቷን ቢያስገምተኝም ለኔም ጥሩ ግዜ ስለነበር ወድያው ምልክቶቻችንን መለዋወጥ ጀመርን ።
የሷን አንድ በአንድ ከሰማሁ በኋላ ፣ የኔንም እንዲሁ ነገርኳት።እንደምልክት አገላለጿ በጣም ውብ ልጅ እንደምትመስል ገምቻለው ።ነገር ግን ከዚህ በፊት ያየኋት ትሆናለች የሚል ሀሳብ አልነበረኝም።
ይቀጥላል
Like 👍 Like 👍
አስተያየት ካሎ በ @atronosebot አድርሱን
:
#አጭር_ልብወለድ
:
ቅዳሜ ከሰአት በኋላ ፣ፀጥ ረጭ ብሏል፣ የቤታችን የግድግዳ ሰአት ብቻ . . .ችው . . . ችው
እያለ በዚህ ፀጥታ ውስጥ ይሰማል። ማንም የለም እኔና እኔ ብቻ። በውስጤ የብቸኝነት ስሜት ተሰማኝ። በዚህ በጠራራ ፀሐይ እቤት ውስጥ ለብቻ መቀመጥ ምን ያህል ይከብዳል እያልኩ ከራሴ ጋር አወራለው።
ዞር ብዬ ክላሲካል ሙዚቃ ሲያሰማ ወደ ነበረው ቴፕ ስመለከት መብራት ሄዶ ዝም እንዳለ ታወቀኝ። ሀሳቤን ሰበሰብኩና በእጄ ወደያዝኩት ልብ ወለድ መፅሀፍ አቀርቅሬ ማንበቤን ቀጠልኩ።
በጥሩ ተመስጦ ውስጥ እንዳለው ድንገት ከአጠገቤ የነበረው ስልክ ጮኸና ቀልቤን ገፈፈው።በጣም ደነገጥኩ። በራሴ መደንገጥ ተገረምኩና እራሴን አረጋግቼ የስልኩን እጀታ በጉጉት አነሳሁት።
<<ሃሎ>> አልኩኝ በትህትና
<<ሄሎ>> አለችኝ አንዲት ልጅ በሚያባባና በሚያምር የድምፅ ቅላፄ።
<<ማንን ፈለጉ ?>>
<<እ. . .ናሆምን ላገኘዉ እችላለሁ ?>>
በዚህን ግዜ የልብ ትርታዬ ፍጥነቱን ጨመረ።
ድምፆም አዲስና የሚማርክ ስለሆነብኝ ማን ልትሆን ትችላለች? በሚል ከራሴ ጋር ትንሽ ተሟገትኩና።
<<ነኝ. . . ማን ልበል?>>
<<. . . ሜሮን እባላለሁ >>
<<ሜሮን?.. .ይቅርታ. . . አላስታወስኩሽም፣ ሜሮን ማን ?>>
<<ሜሮን አለሙ>>
አሁንም ፈፅሞ ላስታውሳት አልቻልኩም።ሜሮን የምትባል ልጅ ፈፅሞ ማወቄን እርግጠኛ አልነበርኩም።
<<በ. .ጣም.. ይቅርታ የኔ እህት አላወኩሽም።>>
<<ይገርምሀል እኔም አላውቅህም።>>
<<የደወልሽው አንቺ መሰለሽኝ?>>
<<አልተሳሳትክም፤ ማለቴ ስልክህን የአስረኛ ክፍል ማስታወሻ ደብተሬ ላይ ከበስተጀርባው ተፅፎ ነው ያገኘሁት።ሁለት አመት እንዳለፈውና በራሴ እጅ ፅሁፍ ስለመፃፉ እርግጠኛ ነኝ ነገር ግን በምን ቀንና ሁኔታ እንደተፃፈ አላስታውሰውም
<<እና?>>
<<እናማ ብዙጊዜ ሲከነክነኝ የነበረ ስልክ ቁጥር ስለነበር ምን አልባት አንተ ካወከኝ በሚል ነበር የደወልኩት።
መልሶን ማመን አቃተኝ።ለሰኮንዶች ያህል በአይኔ የማውቃቸውን እንስቶች በአይነ ህሊናዬ እየቃኘኋቸው ድምፅን ከምስል ጋር ለማዛመድ ሞከረኩ።ሆኖም በፍፁም ልትመጣልኝ አልቻለችም ።በርግጥ ከሁለት አመት በፊት ስለተከሰተ ነገር ማስታወስ ይከብዳል።
የቀረን ነገር ቢኖር በግምት ልንተዋወቅበት የምንችልበትን ሁኔታ መመርመር ነውና ስለየግል ህይታችን መነጋገር ጀመርን።ስለ ት/ቤትና ስለመኖርያ ስፍራችን፣ ስለቤተሰብ እንዲሁም ስለ ቅርብ ጓደኞቻችን ሳይቀር በግልፅ ተወያየን።በሚገር ሁኔታ ግን አሁንም ከጥርጣሬ ያለፈ እዚህ ቦታ ይሆናል ብለን መወሰን ተቸገርን።
ለቀልድ ነው ብዬ እንኳን እንዳልጠረጥራት የምትሰጠኝ መልሶች ሁሉ ግልፅና ፈጣን ነበሩ።
በተለይ ከንግግሯ በራስ መተማመንና በሳልነቷን ለመገመት ይቻል ነበር።ሁኔታው ቢያስገርመኝም ቀስ በቀስ ምርመራውን ትተን ስለየጎል ህይወታችን ገብተነሰ መጨዋወት ጀመርን።
<<ምን አየሰራሽ ነው አሁን?>>
<<ያው አስረኛ ከጨረስኩ በኋላ የሁለት አመት አካውንቲንግ ፊልድ ተምሬ ነግል ድርጅት ውስጥ በመስራት ላይ ነኝ። አንተስ?>>
<<እኔ እንደምንም የመሰናዶ ትምህርት ተምሬ አ.አ.ዮ የአስተዳደር ትምህርት በመማር ላይ ነኝ>>
<<ኦው ጎበዝ ተማሪ ነሃ . . .!>>
<<ነኝ ብለሽ ነው . . . ለመሆኑ ግን ምን ከይነት ሰው ነሽ ማለቴ መልክሽን?>>
<<...እኔጃ ለመግለፅ ይከብዳል።>> ሳቅ እያለች።
<<ታድያ.... ለምን በአካል አንገናኝም፤ >>ምን አልባት በመልክ ልንተዋወቅ እንችላለን?
ጥያቄውን በድፍረት ነበር ያነሳሁት ፤ሆኖም በፍርሀቴ ልክ መልኳን ለማየት ጉጉቱ ነበረኝ። እርሷም በመግደርደር ይሁን አላውቅም።
<<..መገናኘቱ እንኳን የሚመች አይመስለኝም።>
<<ለምን?>>
<<እኔንጃ?>>
<<ፈራሽ እንዴ?>>
<<አይ መፍራት ሳይሆን ሰሞኑን ክፍት ሰአት ስለሌለኝ ነው።>>
ንግግሯ እንደማቅማማት አይነት ነበር ፤ እርግጠኛ አልነበረችም።
<<እሺ. . . ብዙ አላስጨንቅሽም ባይሆን ስልክሽን ስጭኝና ተደዋውለን ሌላ ግዜ እንገናኛለን።>>
ለተወሰኑ ሰኮንዶች ዝም አለች።የኔንም ግራ መጋባት ጥርጣሬ አጎላችው።
<<ምነው ዝም አልሽ?>>
<<...ስልክም አሁን ልሰጥክ አልችልም።>>
<<እህ..ያሁሉ የግል መረጃሽን በግልፅነት ስትነግሪኝ ቆይተሽ እንዴትስልክ መስጠት ከበደሽ?>>
<<በፍፁም መደበቄ አይደለም።በዚህን ሰአት እኔን የምታገኝበት ስልክ ምን አልባት ለሁለት ቀን ብቻ የሚቆይ ነው ። ሌላ ስልክ በሌላ ግዜ እንጂ አሁን ልሰጥክ አልችልም ወይም አላውቀውም።>>
<<አሀ ገባኝ፣ ቤት ልትቀይሩ ነው አይደል?>>
<<አረ አይደለም >>ሳቅ እያለች ነበር።
<<ምንድን ነው እሱ ግልፅ ሁኚ እንጂ የደበቅሽው ነገር ኦንዳለ ይሰማኛል።>>
<<በቃ ለምን ነገ ወደ ማታ አንገናኝም?>>
የአቋም ለዉጧ አስገርሞኛል፣አስደንግጦኛልም።
አሁን ለመናገር ያልፈለገችው ሚስጥሯም ከልብ አጓጓኝ።
<<ጥሩ የት እንገናኝ?>>
<<ፒያሳ ያለው ቤቲ ካፌ ይመችካል?>>
<<ደስ ይለኛል ስንት ሰአት?>>
<<አስራ ሁለት ሰአት።>>
የሰአት ምርጫዋ ወደ ማታ መሆኑ አይናፋርነቷን ቢያስገምተኝም ለኔም ጥሩ ግዜ ስለነበር ወድያው ምልክቶቻችንን መለዋወጥ ጀመርን ።
የሷን አንድ በአንድ ከሰማሁ በኋላ ፣ የኔንም እንዲሁ ነገርኳት።እንደምልክት አገላለጿ በጣም ውብ ልጅ እንደምትመስል ገምቻለው ።ነገር ግን ከዚህ በፊት ያየኋት ትሆናለች የሚል ሀሳብ አልነበረኝም።
ይቀጥላል
Like 👍 Like 👍
አስተያየት ካሎ በ @atronosebot አድርሱን
👍13
#ማፍቀር_ወይስ_መለየት(የመጨረሻ ክፍል)
:
..ሰአቴን አስር ጊዜ አያለው፤ከካፌው በረንዳ ላይ ሆኜ ሜሮን ምን ልትመስል እንደምትችል አሰላስላለው።ፍርሃቴም እንዳለ ነው።አይኔ ግራና ቀኙን ካሁን ካሁን መጣች በሚል ያለመታከት ይማትራል።ብዙ ሴቶች ሲያልፉ እያየሁ እደነግጣለው።በተለይ አንዷማ ራሷ መስላኝ ከመቀመጫዬ ብድግ ለማለት ምንም አልቀረኝ።መልሼ ደግሞ ሰአቱ እየገፋ ሲሄድ የምሞኝ መሰለኝ።
<<ቆይ እስቲ አንድ ሰው እየተጫወተብኝ ቢሆንስ?>> እያልኩ እራሴን በጥርጣሬ እሞግታለሁ ።
ብዙም አልቆየ አይኔ ሳያስበዉ ከአንድ ሰው አይን ጋር ተጋጨ።ሁሉ ነገር በሰከንድ ውስጥ ተቀያየረ።
ዞማ ፀጉር፣ጠይም መልከመልካም፣ቁመናዋ የሚማርክ በተለይ አይኗ! ምንም እንኳን በትክክል ምልክቶቿን ብታሟላም፣እርሷም ቢሆን ወደኔ እየቀረበች ቢሆንም እሷናት ብዬ ለማመን አልቻልኩም ነበር።
<<ባልሳሳት ናሆም የምትባል አንተ ነህ?>>
በካፌ ውስጥ ብዙ ወንዶች እያሉ እኔን ለይታ ማወቋ ገርሞኛል።
<<አልተሳሳትሽም . . .እራስሽ ነሽ ግን?>>
<<አይ እህቷ ነኝ!>> ስትል ቀለደችብኝ።
ፈገግታዋ ልዩ ነበር።
ለረጅም ጊዜ እንደሚተዋወቅ ሰው ጉንጭ ለጉንጭ ተሳሳምን።
የካፌው ሰዎች ሁሉ ወደኛ በመመልከታቸው ኩራት ኩራት አለኝ።
እንድትቀመጥ ከጋበዝኳት በኋላ አስተናጋጁን ጠራሁት።
<<. . . እሺ አስታወስከኝ ?>> በአትኩሮት እያየችኝ ነበር።
<<አረ በፍፁም!ለመሆኑ እንዳንቺ አይነት ሰው እዚህ ከተማ አለ?>>
<<እኔም እንዳተው ነኝ ግን እርገጠኛ አይደለሁም እንጂ መልክህ አዲስ አልሆነብኝም>>
<<ታድያ ስልኩ ከየት ተፃፈ ይባላል?>>
<<እኔም ደንቆኛል...ምን አልባት መንገድ ላይ ይሆን?>>
<<የምታስታውሽው አጋጣሚ አለ?>>
<<ኦው . . ይከብዳል ።>>
<<በርግጥ ልክ ነሽ . . .የእግዜር ስራ ይገርማል።>>
ለጥቂት ሰኮንዶች ዝምታ ሰፈነ።በካፌው ውስጥ ለስለስ ብሎ የኤፍሬም የድሮ ዜማ ተከፍቷል።ትንሽ እንደቆየን ፀጥታውን ሰብርን ስለየግል ህይወታችን ፣ስለመሀበራዊ ጉዳይ መጨዋወት ጀመርን።ቀስ በቀስ ፍርሀቴ ተጠራርጎ ወጣና ስለምንወደውና ትርፍ ጊዜን ስለምናሳልፍበት ሁኔታ ሳይቀር ተነጋግርን።በደቂቃ ውስጥም አንድ ስንሆን ተሰማኝ።ፍቅር እንዳይዘኝም ሰጋሁ።ግን ፈርቼም እንደማይቀርልኝ አውቃለው።ብቻ ቆይታችን በጣም ስለተመቸኝ ጊዜው እንዳይሮጥ አምላኬን ተማፀንኩት።ንግግሯም ጣፋጭ ስለነበር ፈፅሞ ፀጥታ እንዲገባ እድል አልሰጠሁም።
<<ጓደኛ አለሽ >> የሚለው ጥያቄ በውስጤ ይብሰለሰል ነበር።ነገር ግን መቸኮሉ ጥሩ እንዳልሆነ አሰብኩ።እንዲህ እንዲህ እያልን ከምሽቱ አንድ ሰአት ሲሆን ሂሳብ ከፈልኩና ከካፌው ወጥተን በእግራችን የፒያሳን ጎዳናን ማቋራጥ ጀመርን።
ምሽቱ ለኔ ውድና መቼም ልረሳው የማልችለው ትዝታን እንደጫረብኝ እርግጠኛ ነበርኩ
ለሷም ቢሆን ከዚህ የተለየ ይሆናል ብዬ አለገምትም።
<<ትላንት ለምንድን ነው ስልኩን የከለከልሽን>>
<<አልተረዳክኝም ማለት ነው>>
<<አዎ ምንም ግልፅ አልሆነኝም።>>
<<ቆይ እንግርሀለው>>
<<መቼ?>>
<<አሁን>>
<<አሁን እኮ አሁን ነው>>
<<ትንሽ ቆይቶ አሁን?>>
ምን እንደሆነ አላውቅም ልቤ ስጋት እየተሰማው እጅ ለእጅ እንደተያያዝን ከሰፈሯ ደረሰን።መለያየታችንም ግድ ነውና ካንድ ቦታ ቆም ብለን ፊት ለፊት በስስት ተያየን።
<<ልንለያይ ነው ማለት ነው?>>አልኳት በሀዘን
<< ምን ይደረግ>>
<<መቼ እንገናኛለን?>>
<<መቼም. . .።>>
<<ለምን?>>
ዝምት ሰፈነ።አምላኬን <<እባክህ ፈጣርዬ ሆይ የሰጠከኝን እድል መልሰህ እንዳትነፍገኝ>> ስል ተማፀንኩት።
<<ይቅርታ አድርግልኝ ናሆም በሰልክ ያልነገርኩክ ድምፅህ እንዲሁም ብስለትክ ሰለማረከኝ ሳላይህ አልሄድም ብዬ ነዉ።ከነገ ወድያ ለኑሮ አባቴ ጋር ወደ ካናዳ መሄዴ ነዉ።እስካሁንም ያልነገርኩህ ጫወታችን እንዳይቀዘቅዝ ሰግቼ ነው። >>
<<. . .ምን! . . . እየቀለድሽ ነው? >>
ነገሮች ሁሉ ሲገለባበጡ ተሰማኝ።የምሰማውን ማመን አቃተኝ።
የሰጋሁት ነገር እውን መሆኑን ስረዳ ተናደድኩ።ህልምም መስሎኝ ለመባነን ቃጣኝ።
<<እየቀለድኩ አደለም ናሆም፤ባንተ ውስጥ ያለው ስሜት በኔም ውስጥ እንዳለ እወቅልኝ። ስልኩን የደወልኩልህ ከስልክ ደብተሬ ላይ ያሉትን ወዳጆቼን ሁሉ ተሰናብቼ የቀረኝ ያንተ ብቻ ነበር። እኔም ቅር እያለኝ ከምሄድ ብዬ ነው የደወልኩት>>
<<ልክ አይደለሽም. . .።>> ሀሞቴ ፍስስ እንዳለ ነበር።
<<እንዴት ናሆም?>>
መልስ መስጠት ከበደኝ፤አንደበቴም ተሳሰረ።ምን እየሆነ እንዳለ፤ምን እንደማደርግ ሁሉ ግራ ገባኝ።ትንሽ እንደቆየን ከሜሮን ጋርም ምንም የቀረኝ ነገር እንደሌለ ተረዳሁ።የመጨረሻ የምትሆነኝን ቃል እንደምንም አምጬ ሰነዘርኩለት።
<<እስቲ አሁን ምን አለበት . .ሳትደውዪ ዝም ብለሽ ብትሄጂ !?. . .>>
ሳልሰናበታት ከቆመችበት ጥያት ወደ ቤቴ ማዝገሜን ቀጠልኩ።
አይኔ ላይ ብዥ ብዥ እያለብኝ ትንሽ እንደተጓዝኩ ከኋላዬ ደርሳ እጄን አጥብቃ ያዘችው።
<<እባክህን ናሆም ተረዳኝ . . .እኔ ምን አጠፋው ምንስ ማድረግ ነበረብኝ። ይሉቁንስ እግዜር ያለመክናይት አላገናኘንምና ልነደሰት ይገባናል።>>
መልስ አልሰጠኋትም።አይኖቼ አይኖቿን ሲመለከቱ ፈዝዤ ቀረሁ ።በዛ ምሽት እንደኮብ ያበራሉ።የምሰማው ድምፅዋ በደምስሬ ሰርፆ መንፈሴን ሲያድሰው ተሰማኝ ።እኔም ከፊትዋ ቆሜ አይን አይኖን እያየው አዳምጣታለው መልስ መስጠት ግን አልፈለኩም።
<<ተረዳከኝ ?ሆን ብዬ ያደረኩት አይደለም።ለምንስ ሆን ብዬ አደርጋለው።ልክ እንዳተው ሁሉ የስልክ ቁጥሩ ሚስጥር ለኔም ሚስጥር ነው። ደግሞ እግዜር በፈጠረው አጋጣሚ አትማረር፤ ሁሉም ለበጎ ነውና።. . .ተናገር እንጂ ለምን ዝም ትላለህ ? በዚ ላይ ስሜታችን አንድ እንደሆነ እገምታለሁ።>>
በረጅሙ ተነፈስኩና ለደቂቃ ሰማይ ሰማዩን ስመለከት ጨረቃን አገኘኋት።በትዝብት ተመለከትኳት።ከዛም ወደራሴ ተመለስኩና በርጋታ ማሰላሰል ጀመርኩ።ምንም እንኳን አጋጣሚው አስገራሚና አሳዛኝ እንዲሁም የማይታመን ቢሆንም፤እውነታውን ተቀብዬ በሰላም መለያየቱ ጥሩ እንደሚሆን አሰብኩ።ሜሮን ላይም ምንም ስህተት ፈልጌ አጣው።
<<ማክሰኞ ጠዋት ነው የምትሄጂው?>>
<<አዎን>>
<<ታድያ ለምን አልሸኝሽም?>>
<<አይሆንም ከቤተሰብ ጋር ስለሆንኩ እንደገና መጨነቅ የለብንም። እዛው እንደደረስኩ በደቂቃ ውስጥ እደውልልካለው >>
<<እርግጠኛ ነሽ?>>
<<አትጠራጠር ላንተ ሳይሆን ለራሴ ስል ነው የምደውለው።>>
<<እጠብቃለው።>>
<<በቃ ደህና ሁን፤በግዜ ቤትክ ግባ።>>
እቅፏ ውስጥ ስታስገባኝ ይባስ ነፍሴ ተደሰተች።ጠረንዋ ካፋንጫዬ ሲቀር ታወቀኝ።ጡቶቿ ከደረቴ ጋር ሲነካኩ ስሜቴ ጣርያ ደርሶ ተመለሰ።በረጅሙ ተነፈስኩና ዳግም የምነገናኝበትን ቀን መናፈቅ ጀመርኩ።
አንድ ነገር ተሰማኝ....አዲስ ህይወት፤አዲስ እስትንፋስ፤ዳግም ውልደት....ግን ምን ያደርጋል የወደድኳት ለት ተለየኋት.....የናፍቆቷን ኑሮ ''ሀ'' ብዬ ልጀምር ነው።
▪️▪️▪️▪️
:
..ሰአቴን አስር ጊዜ አያለው፤ከካፌው በረንዳ ላይ ሆኜ ሜሮን ምን ልትመስል እንደምትችል አሰላስላለው።ፍርሃቴም እንዳለ ነው።አይኔ ግራና ቀኙን ካሁን ካሁን መጣች በሚል ያለመታከት ይማትራል።ብዙ ሴቶች ሲያልፉ እያየሁ እደነግጣለው።በተለይ አንዷማ ራሷ መስላኝ ከመቀመጫዬ ብድግ ለማለት ምንም አልቀረኝ።መልሼ ደግሞ ሰአቱ እየገፋ ሲሄድ የምሞኝ መሰለኝ።
<<ቆይ እስቲ አንድ ሰው እየተጫወተብኝ ቢሆንስ?>> እያልኩ እራሴን በጥርጣሬ እሞግታለሁ ።
ብዙም አልቆየ አይኔ ሳያስበዉ ከአንድ ሰው አይን ጋር ተጋጨ።ሁሉ ነገር በሰከንድ ውስጥ ተቀያየረ።
ዞማ ፀጉር፣ጠይም መልከመልካም፣ቁመናዋ የሚማርክ በተለይ አይኗ! ምንም እንኳን በትክክል ምልክቶቿን ብታሟላም፣እርሷም ቢሆን ወደኔ እየቀረበች ቢሆንም እሷናት ብዬ ለማመን አልቻልኩም ነበር።
<<ባልሳሳት ናሆም የምትባል አንተ ነህ?>>
በካፌ ውስጥ ብዙ ወንዶች እያሉ እኔን ለይታ ማወቋ ገርሞኛል።
<<አልተሳሳትሽም . . .እራስሽ ነሽ ግን?>>
<<አይ እህቷ ነኝ!>> ስትል ቀለደችብኝ።
ፈገግታዋ ልዩ ነበር።
ለረጅም ጊዜ እንደሚተዋወቅ ሰው ጉንጭ ለጉንጭ ተሳሳምን።
የካፌው ሰዎች ሁሉ ወደኛ በመመልከታቸው ኩራት ኩራት አለኝ።
እንድትቀመጥ ከጋበዝኳት በኋላ አስተናጋጁን ጠራሁት።
<<. . . እሺ አስታወስከኝ ?>> በአትኩሮት እያየችኝ ነበር።
<<አረ በፍፁም!ለመሆኑ እንዳንቺ አይነት ሰው እዚህ ከተማ አለ?>>
<<እኔም እንዳተው ነኝ ግን እርገጠኛ አይደለሁም እንጂ መልክህ አዲስ አልሆነብኝም>>
<<ታድያ ስልኩ ከየት ተፃፈ ይባላል?>>
<<እኔም ደንቆኛል...ምን አልባት መንገድ ላይ ይሆን?>>
<<የምታስታውሽው አጋጣሚ አለ?>>
<<ኦው . . ይከብዳል ።>>
<<በርግጥ ልክ ነሽ . . .የእግዜር ስራ ይገርማል።>>
ለጥቂት ሰኮንዶች ዝምታ ሰፈነ።በካፌው ውስጥ ለስለስ ብሎ የኤፍሬም የድሮ ዜማ ተከፍቷል።ትንሽ እንደቆየን ፀጥታውን ሰብርን ስለየግል ህይወታችን ፣ስለመሀበራዊ ጉዳይ መጨዋወት ጀመርን።ቀስ በቀስ ፍርሀቴ ተጠራርጎ ወጣና ስለምንወደውና ትርፍ ጊዜን ስለምናሳልፍበት ሁኔታ ሳይቀር ተነጋግርን።በደቂቃ ውስጥም አንድ ስንሆን ተሰማኝ።ፍቅር እንዳይዘኝም ሰጋሁ።ግን ፈርቼም እንደማይቀርልኝ አውቃለው።ብቻ ቆይታችን በጣም ስለተመቸኝ ጊዜው እንዳይሮጥ አምላኬን ተማፀንኩት።ንግግሯም ጣፋጭ ስለነበር ፈፅሞ ፀጥታ እንዲገባ እድል አልሰጠሁም።
<<ጓደኛ አለሽ >> የሚለው ጥያቄ በውስጤ ይብሰለሰል ነበር።ነገር ግን መቸኮሉ ጥሩ እንዳልሆነ አሰብኩ።እንዲህ እንዲህ እያልን ከምሽቱ አንድ ሰአት ሲሆን ሂሳብ ከፈልኩና ከካፌው ወጥተን በእግራችን የፒያሳን ጎዳናን ማቋራጥ ጀመርን።
ምሽቱ ለኔ ውድና መቼም ልረሳው የማልችለው ትዝታን እንደጫረብኝ እርግጠኛ ነበርኩ
ለሷም ቢሆን ከዚህ የተለየ ይሆናል ብዬ አለገምትም።
<<ትላንት ለምንድን ነው ስልኩን የከለከልሽን>>
<<አልተረዳክኝም ማለት ነው>>
<<አዎ ምንም ግልፅ አልሆነኝም።>>
<<ቆይ እንግርሀለው>>
<<መቼ?>>
<<አሁን>>
<<አሁን እኮ አሁን ነው>>
<<ትንሽ ቆይቶ አሁን?>>
ምን እንደሆነ አላውቅም ልቤ ስጋት እየተሰማው እጅ ለእጅ እንደተያያዝን ከሰፈሯ ደረሰን።መለያየታችንም ግድ ነውና ካንድ ቦታ ቆም ብለን ፊት ለፊት በስስት ተያየን።
<<ልንለያይ ነው ማለት ነው?>>አልኳት በሀዘን
<< ምን ይደረግ>>
<<መቼ እንገናኛለን?>>
<<መቼም. . .።>>
<<ለምን?>>
ዝምት ሰፈነ።አምላኬን <<እባክህ ፈጣርዬ ሆይ የሰጠከኝን እድል መልሰህ እንዳትነፍገኝ>> ስል ተማፀንኩት።
<<ይቅርታ አድርግልኝ ናሆም በሰልክ ያልነገርኩክ ድምፅህ እንዲሁም ብስለትክ ሰለማረከኝ ሳላይህ አልሄድም ብዬ ነዉ።ከነገ ወድያ ለኑሮ አባቴ ጋር ወደ ካናዳ መሄዴ ነዉ።እስካሁንም ያልነገርኩህ ጫወታችን እንዳይቀዘቅዝ ሰግቼ ነው። >>
<<. . .ምን! . . . እየቀለድሽ ነው? >>
ነገሮች ሁሉ ሲገለባበጡ ተሰማኝ።የምሰማውን ማመን አቃተኝ።
የሰጋሁት ነገር እውን መሆኑን ስረዳ ተናደድኩ።ህልምም መስሎኝ ለመባነን ቃጣኝ።
<<እየቀለድኩ አደለም ናሆም፤ባንተ ውስጥ ያለው ስሜት በኔም ውስጥ እንዳለ እወቅልኝ። ስልኩን የደወልኩልህ ከስልክ ደብተሬ ላይ ያሉትን ወዳጆቼን ሁሉ ተሰናብቼ የቀረኝ ያንተ ብቻ ነበር። እኔም ቅር እያለኝ ከምሄድ ብዬ ነው የደወልኩት>>
<<ልክ አይደለሽም. . .።>> ሀሞቴ ፍስስ እንዳለ ነበር።
<<እንዴት ናሆም?>>
መልስ መስጠት ከበደኝ፤አንደበቴም ተሳሰረ።ምን እየሆነ እንዳለ፤ምን እንደማደርግ ሁሉ ግራ ገባኝ።ትንሽ እንደቆየን ከሜሮን ጋርም ምንም የቀረኝ ነገር እንደሌለ ተረዳሁ።የመጨረሻ የምትሆነኝን ቃል እንደምንም አምጬ ሰነዘርኩለት።
<<እስቲ አሁን ምን አለበት . .ሳትደውዪ ዝም ብለሽ ብትሄጂ !?. . .>>
ሳልሰናበታት ከቆመችበት ጥያት ወደ ቤቴ ማዝገሜን ቀጠልኩ።
አይኔ ላይ ብዥ ብዥ እያለብኝ ትንሽ እንደተጓዝኩ ከኋላዬ ደርሳ እጄን አጥብቃ ያዘችው።
<<እባክህን ናሆም ተረዳኝ . . .እኔ ምን አጠፋው ምንስ ማድረግ ነበረብኝ። ይሉቁንስ እግዜር ያለመክናይት አላገናኘንምና ልነደሰት ይገባናል።>>
መልስ አልሰጠኋትም።አይኖቼ አይኖቿን ሲመለከቱ ፈዝዤ ቀረሁ ።በዛ ምሽት እንደኮብ ያበራሉ።የምሰማው ድምፅዋ በደምስሬ ሰርፆ መንፈሴን ሲያድሰው ተሰማኝ ።እኔም ከፊትዋ ቆሜ አይን አይኖን እያየው አዳምጣታለው መልስ መስጠት ግን አልፈለኩም።
<<ተረዳከኝ ?ሆን ብዬ ያደረኩት አይደለም።ለምንስ ሆን ብዬ አደርጋለው።ልክ እንዳተው ሁሉ የስልክ ቁጥሩ ሚስጥር ለኔም ሚስጥር ነው። ደግሞ እግዜር በፈጠረው አጋጣሚ አትማረር፤ ሁሉም ለበጎ ነውና።. . .ተናገር እንጂ ለምን ዝም ትላለህ ? በዚ ላይ ስሜታችን አንድ እንደሆነ እገምታለሁ።>>
በረጅሙ ተነፈስኩና ለደቂቃ ሰማይ ሰማዩን ስመለከት ጨረቃን አገኘኋት።በትዝብት ተመለከትኳት።ከዛም ወደራሴ ተመለስኩና በርጋታ ማሰላሰል ጀመርኩ።ምንም እንኳን አጋጣሚው አስገራሚና አሳዛኝ እንዲሁም የማይታመን ቢሆንም፤እውነታውን ተቀብዬ በሰላም መለያየቱ ጥሩ እንደሚሆን አሰብኩ።ሜሮን ላይም ምንም ስህተት ፈልጌ አጣው።
<<ማክሰኞ ጠዋት ነው የምትሄጂው?>>
<<አዎን>>
<<ታድያ ለምን አልሸኝሽም?>>
<<አይሆንም ከቤተሰብ ጋር ስለሆንኩ እንደገና መጨነቅ የለብንም። እዛው እንደደረስኩ በደቂቃ ውስጥ እደውልልካለው >>
<<እርግጠኛ ነሽ?>>
<<አትጠራጠር ላንተ ሳይሆን ለራሴ ስል ነው የምደውለው።>>
<<እጠብቃለው።>>
<<በቃ ደህና ሁን፤በግዜ ቤትክ ግባ።>>
እቅፏ ውስጥ ስታስገባኝ ይባስ ነፍሴ ተደሰተች።ጠረንዋ ካፋንጫዬ ሲቀር ታወቀኝ።ጡቶቿ ከደረቴ ጋር ሲነካኩ ስሜቴ ጣርያ ደርሶ ተመለሰ።በረጅሙ ተነፈስኩና ዳግም የምነገናኝበትን ቀን መናፈቅ ጀመርኩ።
አንድ ነገር ተሰማኝ....አዲስ ህይወት፤አዲስ እስትንፋስ፤ዳግም ውልደት....ግን ምን ያደርጋል የወደድኳት ለት ተለየኋት.....የናፍቆቷን ኑሮ ''ሀ'' ብዬ ልጀምር ነው።
▪️▪️▪️▪️
👍8❤2
#ሆሆ
“ወንድ ሆኖ የማያመነዝር ፤ ወታደር ሆኖ እማይሰነዝር ፤ ነጋዴ ሆኖ እማይዘረዝር የለም ! “ይላል ምኡዝ።
እውነቱን ነው፤ከጥቂቶቻችን በቀር ብዙ ወንድ በህይወቱ ቢያንስ አንዴ በትዳሩ ላይ ያድጠዋል። ድርያ በአርቲስት ላይ ይጋነናል እንጂ ፊትና ጭን ከተሰጠው፤ ገበሬ ነጋዴ ፓስተር ሼህ የንስሃ አባት ሳይቀር እንደሚወሰልት እናውቃለን። መቸም የሴት ገላ ማቀፍ እንዴት እንደሚጥም የቀመሰ ያውቀዋል፤ ግን የሚያስከፍለው ዋጋ ከደስታው ጋር አይመጣጠንም፤ አንድ ጣሳ ደስታ ይሰጥህና አንድ በርሚል ጣጣ ያሸክምሃል!!
#አንድ
የሆነ ጊዜ ላይ አሜሪካ ውስጥ ባንድ ከተማ የተከሰተውን ዜና በራሴ መንገድ ስተርተው ይሄን ይመስላል፤
ሰውየው ሚስቱ ማታ ለስራ በሄደችበት ውሽማውን አምጥቶ በተቀደሰው አልጋ ላይ ይፈትጋታል፤ በፍትጊያ መሀል ኮቴ ሰምቶ ቀና ሲል ሚስቱን አያት፤ ውሽምየዋ እንደስፓይደር ውመን በመስኮት ዘልላ ነካችው፤ ባልየው ብቻውን ከሚስቱ ጋር ተፋጠጠ፤ ሚስትዮዋ ለሰይፍ ሩብ ጉዳይ የቀረው ቢላዋ ይዛለች፤ ባሉካ ለመሮጥ ተመኜ ፤ግን እግሩ ቀጤማ ሆነበት፤ በወዛደር አማርኛ እንግለፀው ከተባለ እድሩ የቡልዶዘር ጎማ ሆነበት፤ ሚስትየው ምንም አላለችም፤ አልጋው ላይ እመርር ብላ ወጣችና አገር አማን ነው ብሎ ቆሞ የሚጠብቀውን ብልቱን ጨብጣ ከስሩ መተረችው፤ ከዛ እንደ ቀይ ስር በቁንጮው አንጠልጥላው ወጣችና በቤቱ ጉዋሮ በሚገኘው ዱር ውስጥ ወርውራው ተሰወረች፤
ብዙ ሳይቆይ አምቡላንስ ስልቡን ሰውየ ይዞ ወድ ሆስፒታ መረሸ፤ ያሜሪካ ፖሊስ በቦታው ደርሶ ፤ ከሲአኤ ጋር በመተባበር አካባቢውን በብረት ለበስ መኪና አጥሮ ተቆርጦ የተጣለውን ወሸላ ፍለጋ ተሰማራ፤፤ ከላይ በሂሊኮፍተር ከታች በአነፍናፊ ውሻ የታገዘ ሰአታትን የፈጀ አሰሳ በሁዋላ የተቆረጠው ብልት የጉንዳን መንጋ ወርሶት ተገኘ፤፤ በመጨረሻ ዶክተሮች ወደ ስልቡ ባል ቀርበው፤ “የጠፋብህ ብልት ይሄ ነውን?” ብለው’ በመስቀልኛ ጥያቄ መርምረው አረጋግጠው፤ በቀዶ ጥገና ተከሉለት፤ትንሽ ከመንሻፈፉ በቀር በድሮው ቦታ ተተከለ ፤እረ እንዴውም ከዱሮው ሳይሻል አይቀርም፤ ሚስት ተብየዋን ደስ አይበላትና ሀኪሞች ፤ እንደ ክንዱ በፈለገ ጊዜ የሚዘረጋውና የሚያጥፈው አድርገው ተከሉለት፤
#ሁለት
ይሄ ደሞ ባልንጀራየ የነገረኝ ነው፤
ዲሲ ውስጥ የሚኖሩ ባልና ሚስት ኢትዮጵያውን የተጋቡበትን አስረኛ አመት በማክበር እየተዝናኑ አመሹ፤ከዚያ ሚስትዮዋ” ቤብ፤ በፍቅራችን ላይ ቅመም የሚጨምር ነገር ላሳይህ ” አለችና ከራቫቱን ፈታችለት፤ አያ ‘ቤብ ‘ ክራቫቱን እያስፈታ ፤ ከታች ስራ እንዳይፈታ፤ ቀበቶውን ፈታ፤
ከጥቂት ደቂቃ በሁዋላ አንድ የትራፊክ ፖሊስ መንገድ ዳር ቆሞ ቫይብሬት የሚያደርግ መኪና ስለተመለከተ ጠጋ ብሎ መስኮቱን አንኩዋኩዋ!
“is there any problem ? officer? “ አለ ባልየው ትንፋሹ እየተቆራረጠ።
“መኪና መሳረር ህገወጥ ስለሆነ ልቀጣችሁ ነው” አለና ፖሊሲ ባልየውን መቶ ዶላር ቀጣው፤ ሚስቲቱን ግን ሁለት መቶ ብር ቅጣት ጣለባት፤
ባልየው ትንሽ ቆይቶ ስለከነከነው ፖሊሱን ተከትሎ ደረሰበትና፤
“ቅጣቱስ ይሁን! ይበለኝ፤ የግሬን ነው ያገኘሁት፤ ግን በምን ምክንያት ነው እኔን መቶ ብር ቀጥተህ ሚስቴን ሁለት መቶ ቀጣሃት?’
ፖሊሱ እንዲህ መለሰ፤
“እ ሷ መኪና ውስጥ እንዲህ አይነት ነገር ስታደርግ ያገኘሁዋት ለሁለተኛ ጊዜ ነው፤ ለዝያ ነው እጥፍ ያስከፈልኩዋት”😳
ባልየው በድንጋጤ ታሞ ይሄው በጎፈንድ ሚ እያስታመምነው እንገኛለን፤
🔘በውቀቱ ስዩም🔘
“ወንድ ሆኖ የማያመነዝር ፤ ወታደር ሆኖ እማይሰነዝር ፤ ነጋዴ ሆኖ እማይዘረዝር የለም ! “ይላል ምኡዝ።
እውነቱን ነው፤ከጥቂቶቻችን በቀር ብዙ ወንድ በህይወቱ ቢያንስ አንዴ በትዳሩ ላይ ያድጠዋል። ድርያ በአርቲስት ላይ ይጋነናል እንጂ ፊትና ጭን ከተሰጠው፤ ገበሬ ነጋዴ ፓስተር ሼህ የንስሃ አባት ሳይቀር እንደሚወሰልት እናውቃለን። መቸም የሴት ገላ ማቀፍ እንዴት እንደሚጥም የቀመሰ ያውቀዋል፤ ግን የሚያስከፍለው ዋጋ ከደስታው ጋር አይመጣጠንም፤ አንድ ጣሳ ደስታ ይሰጥህና አንድ በርሚል ጣጣ ያሸክምሃል!!
#አንድ
የሆነ ጊዜ ላይ አሜሪካ ውስጥ ባንድ ከተማ የተከሰተውን ዜና በራሴ መንገድ ስተርተው ይሄን ይመስላል፤
ሰውየው ሚስቱ ማታ ለስራ በሄደችበት ውሽማውን አምጥቶ በተቀደሰው አልጋ ላይ ይፈትጋታል፤ በፍትጊያ መሀል ኮቴ ሰምቶ ቀና ሲል ሚስቱን አያት፤ ውሽምየዋ እንደስፓይደር ውመን በመስኮት ዘልላ ነካችው፤ ባልየው ብቻውን ከሚስቱ ጋር ተፋጠጠ፤ ሚስትዮዋ ለሰይፍ ሩብ ጉዳይ የቀረው ቢላዋ ይዛለች፤ ባሉካ ለመሮጥ ተመኜ ፤ግን እግሩ ቀጤማ ሆነበት፤ በወዛደር አማርኛ እንግለፀው ከተባለ እድሩ የቡልዶዘር ጎማ ሆነበት፤ ሚስትየው ምንም አላለችም፤ አልጋው ላይ እመርር ብላ ወጣችና አገር አማን ነው ብሎ ቆሞ የሚጠብቀውን ብልቱን ጨብጣ ከስሩ መተረችው፤ ከዛ እንደ ቀይ ስር በቁንጮው አንጠልጥላው ወጣችና በቤቱ ጉዋሮ በሚገኘው ዱር ውስጥ ወርውራው ተሰወረች፤
ብዙ ሳይቆይ አምቡላንስ ስልቡን ሰውየ ይዞ ወድ ሆስፒታ መረሸ፤ ያሜሪካ ፖሊስ በቦታው ደርሶ ፤ ከሲአኤ ጋር በመተባበር አካባቢውን በብረት ለበስ መኪና አጥሮ ተቆርጦ የተጣለውን ወሸላ ፍለጋ ተሰማራ፤፤ ከላይ በሂሊኮፍተር ከታች በአነፍናፊ ውሻ የታገዘ ሰአታትን የፈጀ አሰሳ በሁዋላ የተቆረጠው ብልት የጉንዳን መንጋ ወርሶት ተገኘ፤፤ በመጨረሻ ዶክተሮች ወደ ስልቡ ባል ቀርበው፤ “የጠፋብህ ብልት ይሄ ነውን?” ብለው’ በመስቀልኛ ጥያቄ መርምረው አረጋግጠው፤ በቀዶ ጥገና ተከሉለት፤ትንሽ ከመንሻፈፉ በቀር በድሮው ቦታ ተተከለ ፤እረ እንዴውም ከዱሮው ሳይሻል አይቀርም፤ ሚስት ተብየዋን ደስ አይበላትና ሀኪሞች ፤ እንደ ክንዱ በፈለገ ጊዜ የሚዘረጋውና የሚያጥፈው አድርገው ተከሉለት፤
#ሁለት
ይሄ ደሞ ባልንጀራየ የነገረኝ ነው፤
ዲሲ ውስጥ የሚኖሩ ባልና ሚስት ኢትዮጵያውን የተጋቡበትን አስረኛ አመት በማክበር እየተዝናኑ አመሹ፤ከዚያ ሚስትዮዋ” ቤብ፤ በፍቅራችን ላይ ቅመም የሚጨምር ነገር ላሳይህ ” አለችና ከራቫቱን ፈታችለት፤ አያ ‘ቤብ ‘ ክራቫቱን እያስፈታ ፤ ከታች ስራ እንዳይፈታ፤ ቀበቶውን ፈታ፤
ከጥቂት ደቂቃ በሁዋላ አንድ የትራፊክ ፖሊስ መንገድ ዳር ቆሞ ቫይብሬት የሚያደርግ መኪና ስለተመለከተ ጠጋ ብሎ መስኮቱን አንኩዋኩዋ!
“is there any problem ? officer? “ አለ ባልየው ትንፋሹ እየተቆራረጠ።
“መኪና መሳረር ህገወጥ ስለሆነ ልቀጣችሁ ነው” አለና ፖሊሲ ባልየውን መቶ ዶላር ቀጣው፤ ሚስቲቱን ግን ሁለት መቶ ብር ቅጣት ጣለባት፤
ባልየው ትንሽ ቆይቶ ስለከነከነው ፖሊሱን ተከትሎ ደረሰበትና፤
“ቅጣቱስ ይሁን! ይበለኝ፤ የግሬን ነው ያገኘሁት፤ ግን በምን ምክንያት ነው እኔን መቶ ብር ቀጥተህ ሚስቴን ሁለት መቶ ቀጣሃት?’
ፖሊሱ እንዲህ መለሰ፤
“እ ሷ መኪና ውስጥ እንዲህ አይነት ነገር ስታደርግ ያገኘሁዋት ለሁለተኛ ጊዜ ነው፤ ለዝያ ነው እጥፍ ያስከፈልኩዋት”😳
ባልየው በድንጋጤ ታሞ ይሄው በጎፈንድ ሚ እያስታመምነው እንገኛለን፤
🔘በውቀቱ ስዩም🔘
👍3
#ኑ_ሀገር_እንስፋ!
ክፍፍል መችነበር፥
በእግዜሩ አሰራር፥በቅድመ አፈጣጠር
ሰው ሰው ብቻ ነበር፥ዘሩ ሳይቆጠር
ሰውነት ተንዶ፥
እንዲህ እንደዛሬ፥ሳይኖር መበታተን
የመቆጣጠር ዛር፥መቃብር ሳይከተን
አንድ እናት ነበረን፥
ቀሚሷ እንደኪዳን፥ሁላችን ምንለብሰው
ዛሬ ተለያይተን፥
ክብሯን እንደ እቃቃ፥ዳቦ ሳንቆርሰው
ሻህላ ወረሰን፥
ውስጣችን ተበላ፥
ፍቅር የጠመቅንበት፥ተሰበረ ጋኑ
ለናታችን ቀሚስ
ጥጥ የነደፍንበት፥ተጣለ ደጋኑ
ሰው ተተነተነ፥ሰው ተቆራረሰ
ዘር ስንቆጣጠር፥ሀገር ፈራረሰ
ፍቅር እንደቁና፥አርጅቶ ተጣለ
ጥላቻ ድንኳኑን፤በላያችን ጣለ
የናታችን ቀሚስ፥
ባለሶስ ቀለሙ፥
በሰማይ ዳስ ሲጥል፥ለምድር የሚያጠላው
ትውልድ ሲናጠቅ፥
በ"የኔ ነው !" "የኔ"፥የጥል እሳት በላው
ይኼው እና ዛሬ!
ያች ሙሉ እመቤት
ያቺ ሸዋ ግርድሽ፥
በክፍፍል ክናድ፥
ከፍቅር ሰገነት፥ከርማ ስትገፋ
እርቃኗን ቆማለች፥
የቃልኪዳን ልብሷን፥ቀሚሷን ተገፋ
ያ ብልህ አያቴ
ትውልድ በሽሚያ፥የቀደደው ልብሷን
ሊሰፋ ይጥራል፥የክብር ቀሚሷን
ስሩ ተቀምጬ፥
በልጅ አእምሮዬ፥ጥያቄ ይዘንባል
በቦዘዙ ዐይኖቹ፥
ክሩ ከመርፌው ጫፍ ላይገባ ይዛባል
እንዲህ ጠይቃለሁ?
ምን ነካህ አባባ፥
ይኼ ቅዳች ቀሚስ፥ዳግም ተጠግኖ
እንደቀድሞው አይጥል፥ውበቱ ጀግኖ?"
ለምን ትለፋለህ፥?ብዬ ስጠይቀው
አያቴ እንዲህ አለኝ፥እንባው እያነቀው
ልጄ ሆይ አድምጪ፥
መስፋቴ ቅኔ ነው፥እንደወርቅ እንደሰም
አላዳውር አይል፥ስንጥቅ ኖሮት ቀሰም
አስተውይ ልጄ፥
መርፌ ማለት ፍቅር፥ሰርስሮ ሚገባ
ክር ማለት ሰላም፥
ቀዳዳን ጠግኖ፥ዳግም ሚገነባ
ይለኛል አያቴ፥
ፍቅር ባለው መርፌ፥ነፍሱ እየተወጋች
ክር ላለው ሰላም፥ደጀን እየተጋች
የእናቴን ቀሚስ
ሲጠግን ስላየሁ፥
እንሆኝ አንድ ቃል!
የናት ክበር ወድቆ፥
የለምና ለክብር፥የሚሰነቅ ተስፋ
ኑ እርቃን እንሸፍን፥ኑ ሀገር እንስፋ
🔘በዳግም ህይወት🔘
ክፍፍል መችነበር፥
በእግዜሩ አሰራር፥በቅድመ አፈጣጠር
ሰው ሰው ብቻ ነበር፥ዘሩ ሳይቆጠር
ሰውነት ተንዶ፥
እንዲህ እንደዛሬ፥ሳይኖር መበታተን
የመቆጣጠር ዛር፥መቃብር ሳይከተን
አንድ እናት ነበረን፥
ቀሚሷ እንደኪዳን፥ሁላችን ምንለብሰው
ዛሬ ተለያይተን፥
ክብሯን እንደ እቃቃ፥ዳቦ ሳንቆርሰው
ሻህላ ወረሰን፥
ውስጣችን ተበላ፥
ፍቅር የጠመቅንበት፥ተሰበረ ጋኑ
ለናታችን ቀሚስ
ጥጥ የነደፍንበት፥ተጣለ ደጋኑ
ሰው ተተነተነ፥ሰው ተቆራረሰ
ዘር ስንቆጣጠር፥ሀገር ፈራረሰ
ፍቅር እንደቁና፥አርጅቶ ተጣለ
ጥላቻ ድንኳኑን፤በላያችን ጣለ
የናታችን ቀሚስ፥
ባለሶስ ቀለሙ፥
በሰማይ ዳስ ሲጥል፥ለምድር የሚያጠላው
ትውልድ ሲናጠቅ፥
በ"የኔ ነው !" "የኔ"፥የጥል እሳት በላው
ይኼው እና ዛሬ!
ያች ሙሉ እመቤት
ያቺ ሸዋ ግርድሽ፥
በክፍፍል ክናድ፥
ከፍቅር ሰገነት፥ከርማ ስትገፋ
እርቃኗን ቆማለች፥
የቃልኪዳን ልብሷን፥ቀሚሷን ተገፋ
ያ ብልህ አያቴ
ትውልድ በሽሚያ፥የቀደደው ልብሷን
ሊሰፋ ይጥራል፥የክብር ቀሚሷን
ስሩ ተቀምጬ፥
በልጅ አእምሮዬ፥ጥያቄ ይዘንባል
በቦዘዙ ዐይኖቹ፥
ክሩ ከመርፌው ጫፍ ላይገባ ይዛባል
እንዲህ ጠይቃለሁ?
ምን ነካህ አባባ፥
ይኼ ቅዳች ቀሚስ፥ዳግም ተጠግኖ
እንደቀድሞው አይጥል፥ውበቱ ጀግኖ?"
ለምን ትለፋለህ፥?ብዬ ስጠይቀው
አያቴ እንዲህ አለኝ፥እንባው እያነቀው
ልጄ ሆይ አድምጪ፥
መስፋቴ ቅኔ ነው፥እንደወርቅ እንደሰም
አላዳውር አይል፥ስንጥቅ ኖሮት ቀሰም
አስተውይ ልጄ፥
መርፌ ማለት ፍቅር፥ሰርስሮ ሚገባ
ክር ማለት ሰላም፥
ቀዳዳን ጠግኖ፥ዳግም ሚገነባ
ይለኛል አያቴ፥
ፍቅር ባለው መርፌ፥ነፍሱ እየተወጋች
ክር ላለው ሰላም፥ደጀን እየተጋች
የእናቴን ቀሚስ
ሲጠግን ስላየሁ፥
እንሆኝ አንድ ቃል!
የናት ክበር ወድቆ፥
የለምና ለክብር፥የሚሰነቅ ተስፋ
ኑ እርቃን እንሸፍን፥ኑ ሀገር እንስፋ
🔘በዳግም ህይወት🔘
👍2
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_አንድ
:
✍ደራሲ ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...የዲላ ከተማ ነዋሪ የሆነችው የ45 አመቷ ወ/ሮ ምንትዋብ በህይወቷ አሥቸጋሪ ግዜ ላይ ትገኛለች።ሀዘን ውሥጧን ሠብሯታል።ስጋት ቅሥሟን ሠልቧታል።ሞራሏንም ንብረቷንም ፍቅሬ ብላ ላሥጠጋችው፤ ትዳሬ ብላ ለተቀበለችው ሰው ቀሥ በቀሥ አስረክባው ነበር። ያ ሰው ግን በዚህ ወቅት ሁሉን ነገር ይዞባት ተሰውሯል...ለንግድ ብሎ እንደወጣ የዉሀ ሽታ ሁኖ ከቀረ እነሆ ሁለት ወራት ደፍኗል...ሶስተኛው እየተጋመሰ ነው።መልዕክት የለ...ሥልክ የለ...ምንም ፍንጭ የሌለው ድፍንፍን ያለ ወጋገን አልባ ጨለማ ስጋት ዙሪያዋን ከቧታል።
ምንትዋብን እንዲህ ስጋት ላይ የጣላት የሶሶት አመት ባለቤትዋ ሁኖ አልጋዋን ሲጋራት የነበረው ወርቅ አለማው ነው።እርግጥ መጀመርያ ከቤት ሲወጣ እንደወትሮው ለተለመደ ሥራ ነበር..ያልተለመደው ሥልክ ደውሎ ያለማወቁ..ከዚያ በፊት ከሚያሳልፈው የሣምንትና የአስራ አምስት ቀን የግዜ ቆይታ ባልተጣጣመ መልኩ ከሁለት ወር በላይ መዘግየቱ ነው።ይዞ የሄደው ንብረት ወይም በእሡ እጅ ያለው ንብረት ቀላል የሚባል አይደለም።ከዛ ውሥጥ ደግሞ 80 ፐርሰንቱ የሷ የግል ንብረት ነው..እረ ምን የሷ ብቻ የአንድዬ ልጇም ንብረት ነው፤ከአባቱ በውርሥ የተላለፈለት..ከሟች ባሏ ጋር በአንድነት ያፈሩት የቤተሠቡ መተዳደርያ ጥሪት ነው..ወደድኩሽ ብሎ ለተጠጋት ባል ነኝ ብሎ እቤቷ ለአመታት ለኖረው ወርቅ አለማው አምናና አሳልፋ የሠጠችው።ወርቅ አለማው የምንትዋብ የበፊት ሟች ባል ተቀጣሪ ሰራተኛ ሁኖ ከአምሥት አመት በላይ የኖረ የ40 አመት ጎልማሳ ነው።ምንትዋብ ከእሡ ጋር የመቀራረብ እድሉ ያጋጠማት የልጇ አባት የሆኑት አዛውንት ባሏ ከሞቱ በሁዋላ በእሳቸው ይተዳደር የነበረውን ሆቴል እሷ መቆጣጠር ስትጀምር ነበር።ምክንያቱም ወርቅ አለማውም የሆቴሉ ስራ-አስኪያጅ ስለነበር በየቀኑ የመገናኘትና የመነጋገር እድል ነበራቸው።ሳያስቡት መቀራረብ ቀስ በቀስ
መሳሳብ ጀመሩ..
ትክክለኛውን ነገር ፈታተን እና ከፋፍለን እንየው ከተባለ ግን ሳያስቡት የሚለው ቃል የሚሠራው ለምንትዋብ ብቻ ነው...ወርቅ አለማው እያንዳንዷን እርምጃውን በእቅድ ነበር ያከናወናት...ቀድሞውንም በፍቅር ስም እየማለ የሚከውነው ከፍቅር ውጭ የሆነ አላማ ነበረው።በፍቅር መሠላልነት በመንጠላጠል ወደ ሀብት ማማ ላይ መንጠልጠል..አዎ ይሄን በልቡ ውስጥ በሚስጥር ቀብሮ ለማንም ትንፍሽ ሳይል በአላማ ሲንቀሳቀስ ነበር።...ያው ጥሩም ሆነ መጥፎ ነገር ሠው ብርቱና የአሸናፊ ሀይል በውስጡ ይዞ የሚዞር የእግዛብሔርን እስትንፋስ የተጋራ ልዩ ፍጡር ነውና ከልቡ ካቀደ..ያቀደውንም እንዲሳካለት ሳይሰለች ከጣረና ከለፋ ይሳካለታልና ይሄው ለሶስት አመት በማድባት ከሠራ በኋዋላ ዛሬ ያሳካው ይመስላል...ክፋቱ ይሄንን እግዛብሔር ከእስትንፋሱ ጋር ደባልቆ የሠጠውን የአሸናፊነት ሀይል በጎ ላልሆነ ነገር ስለተጠቀመበት(ተጠቅሞበት ከሆነ ማለቴ ነው)እንዴት ነው የሚቀጣው......? አዎ ምንትዋብ ዛሬ ነገሮች ከእጇ ሾልከው ያመለጡ ከመሠሉ በሁዋላ ነው አይኖቿ በድርበቡም ቢሆን የተከፈቱላት እና ልቦናዋም በጥርጣሬ ይታመሥ የጀመረው... ...እርግጥ አሁን ሥጋት ነው እንጂ ምንም የሚታወቅና የተረጋገጠ ነገር የለም።እውነት በውስጧ እንደጠረጠረሽው ከድቷት ይሆን ወይስ በሄደበት ሀገር አደጋ አጋጥሞት.. ...?ሌባ ዘርፎት ወይስ ሽፍታ ገድሎ አንድ ስርቻ ጥሎት? እግዜር ነው የሚያውቀው።ምንትዋብ ማለቂያ የሌላቸው ግትልትል ሀሳቦቿን በአእምሮዋ ስታመላልስ ቆይታ ድንገት እንደመባነን ብላ ወደ ቀልቧ ስትመለስ የ29 አመቱ ወጣት የፖሊስ መኮንን ልጇ ስሯ ተንበርክኮ አይን አይኗን በሀዘኔታ እያያት ትካዜዋን ሲጋራት ተመለከተች......
<<የኔ ውሻ>>አለችው እጇን ግንባሩ ላይ ጭና
<<አቤት እማ>>
<<የምሳ ሰአት ደርሶ ነው የመጣኸው? ምን አንበረከከህ ደግሞ..? ለምን አትነሳም?>>
<<አዎ 7 ሰአት ሊሆንኮ ነው...ጠዋት ትቼሽ የሄድኩበት ቦታ ሳገኝሽኮ ደነገጥኩ>> በማለት ከተንበረከከበት በመነሳት ከጎኗ ሶፋው ላይ ተቀመጠና መናገር ጀመረ
<<እማ ያንቺ ስጋት ሙሉ በሙሉ ግልፅ አልሆነልኝም..ለስራ ነው የወጣው አይደል...? ለዚያውም ጅቡቲ ድረስ...እርቀቱን አስቢው የቆየበትን ግዞኮ ያን ይህል ተስፋ የሚቆረጥበት አይደለም...ሶስት አራት ወር የሚቆይበት ጉዳይ ሊያጋጥመው ይችላል>>እናቱን ለማፅናናት ብሎ እንጂ ሰውዬው ያለምንም ነገር ድምጹን አጥፍቶ ይሄን ያህል ግዜ እንዳልቆየ የሱም ልብ ጠርጥሯል።
<<መቆየቱ አይደለም ያስጨነቀኝ።ባልተለመደ መልኩ ለአንድ ቀንም ቢሆን ያለመደወሉ...ስልኩም ጥሪ ያለመቀበሉ ነው ያሳሰበ ኝ....በቃ ውስጤ ፈርቷል ።>>አለችው ከአይኖቿ ያለፍላጎቷ የሚረግፈውን እንባ በእጆቿ እየጠራረገች
<<እርግጥ መደወል ነበረበት...ሳይመቸው ቀርቶ ይሆናል።ወይንም የሡ አለመደወል እኛን ይሄን ያህል ያስጨንቃቸዋል ብሎ ስላላሠበም ሊሆን ይችላል።>>
ምንትዋብ ከተቀመጠችበት ተነሳች...በአንድ እጇ ወገቧን ይዛ በሌላ እጆ የተንጨፈረረ ፀጉሯን ይበልጥ እንዲንጨፋረር እያፍተለተለች ንግግሯን ቀጠለች<<አዎ..እሡን እንኳን እውነትህን ነው..አጅሬ ምን ጎደለበት? እስቲ ተወኝ..ጉድ ሳያደርገኝ አልቀረም...በውስጤ እሳት እየተንቀለቀለ ነው።አሁን ትንሽ እረፍት ልውሰድ....>>ብላ እግሮቿን እየጎተተች ሳሎኑን ለቀቀችና ወደ መኝታ ቤቷ ሄደች።
ኮማንደር መሀሪ የእናቱን ወደ መኝታ ቤቷ ገብታ በራፉን ከውስጥ መቀርቀሯን ከተመለከተ በሁዋላ ከኪሱ ሞባይሉን አወጣና ደወለ...ፍቅረኛው ጋር።
የእናቱ ጭንቀት የሱም ጭንቀት ሆኗል...ከዚህ ጭንቀቱ ረገብ እንዲል ደግሞ ወደ ሥራ ከመግባት ይልቅ ፍቅረኛውን ማግኘት ይሻለዋል። ከአምስት ጥሪ በሁዋላ ስልኩ ተነሳ።ግን እሷ አልነበረችም ያነሳችው ታናሽ እህቷ ነበረች።
ሞባይሏን እቤት ጥላ እንደወጣችና እቤት እንደሌለች ነገረችው...ምንም አላላትም ስትመጣ እንድትደውልለት መልእክት አስቀምጦላት ስልኩን ዘጋው።
<<ይቺ ደግሞ ሲፈልጓት ሁሌ የማትገኝ ሰበበ ብዙ የሆነች የልብ በሽታ ነች>>ብስጭቱ ሳያስበው ድምጽ አውጥቶ እንዲነጫነጭ እስገደደው።ደግነቱ ሳሎኑ ውስጥ ለብቻው ስለሆነ የሰማው ሰው አልነበረም።
ምን ማድረግ እንዳለበት ባለማወቅና ግራ በመጋባት ክፍሉ ውስጥ መንጎራደድ ጀመረ ሁሉ ነገር አስጠላው።ይሄን ወርቅ አለማው የተባለውን አባቱ ከሞተ በሁዋላ የእናቱ ባል ሆኖ እቤታቸው ለሶስት አመት የኖረውን ሠውዬ ከመጀመርያው አንስቶ ቀልቡ ወዶትና ልቡም ተቀብሎት አያውቅም ነበር..ግን ለእናቱ ካለው ክብርና ፍቅር የተነሳ ከአንደበቱ ቃላት አውጥቶ ተቃውሞውን ገልጾ ወይም ፊቱን በማጨማደድ ያለመፈለግ ስሜቱን አሳውቆ አያውቅም ነበር...እንዴት ብሎ እናቱን<<እማዬ የእንጀራ አባቴን አልወደድኩትም..ጥሩ ባል አልመረጥሽም...ይቅርብሽ>>ሊላት ይችላል? በፍጹም እንደዛ ማድረግ አይቻለውም።አስተዳደጉም ያንን አይፈቅድለትም።በዚህ ምድር ላይ በጣም የሚያፈቅረውና በዛውም ልክ የሚፈራው ሰው ቢኖር እናቱን ነው።
ቢሆንም ግን ሁልግዜ አንድ ቀን አንድ ነገር እንደሚከሰት ይጠረጥር ነበር...አሁን ያ ጥርጣሬው በአስፈሪ መልኩ እውን ሳይሆን አልቀረም<<መሀሪ>>ከኪችን አከባቢ የመጣ የጥሪ ድምጽ ከሰመጠበት ሀሳብ ውስጥ መዞ አወጣው።መስታወት ነበረች።መስታወት የ25 አመት የጎመራች ወጣት ስትሆን በቤታቸው ከ12 አመት በላይ የኖረች ሠራተኛችው ነች...ለነገሩ እንዲሁ ስሙ ነው እንጂ ሠራተኛ ከማለት የማደጎ ልጃቸው ነች ማለት ይቀላል
:
#ክፍል_አንድ
:
✍ደራሲ ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...የዲላ ከተማ ነዋሪ የሆነችው የ45 አመቷ ወ/ሮ ምንትዋብ በህይወቷ አሥቸጋሪ ግዜ ላይ ትገኛለች።ሀዘን ውሥጧን ሠብሯታል።ስጋት ቅሥሟን ሠልቧታል።ሞራሏንም ንብረቷንም ፍቅሬ ብላ ላሥጠጋችው፤ ትዳሬ ብላ ለተቀበለችው ሰው ቀሥ በቀሥ አስረክባው ነበር። ያ ሰው ግን በዚህ ወቅት ሁሉን ነገር ይዞባት ተሰውሯል...ለንግድ ብሎ እንደወጣ የዉሀ ሽታ ሁኖ ከቀረ እነሆ ሁለት ወራት ደፍኗል...ሶስተኛው እየተጋመሰ ነው።መልዕክት የለ...ሥልክ የለ...ምንም ፍንጭ የሌለው ድፍንፍን ያለ ወጋገን አልባ ጨለማ ስጋት ዙሪያዋን ከቧታል።
ምንትዋብን እንዲህ ስጋት ላይ የጣላት የሶሶት አመት ባለቤትዋ ሁኖ አልጋዋን ሲጋራት የነበረው ወርቅ አለማው ነው።እርግጥ መጀመርያ ከቤት ሲወጣ እንደወትሮው ለተለመደ ሥራ ነበር..ያልተለመደው ሥልክ ደውሎ ያለማወቁ..ከዚያ በፊት ከሚያሳልፈው የሣምንትና የአስራ አምስት ቀን የግዜ ቆይታ ባልተጣጣመ መልኩ ከሁለት ወር በላይ መዘግየቱ ነው።ይዞ የሄደው ንብረት ወይም በእሡ እጅ ያለው ንብረት ቀላል የሚባል አይደለም።ከዛ ውሥጥ ደግሞ 80 ፐርሰንቱ የሷ የግል ንብረት ነው..እረ ምን የሷ ብቻ የአንድዬ ልጇም ንብረት ነው፤ከአባቱ በውርሥ የተላለፈለት..ከሟች ባሏ ጋር በአንድነት ያፈሩት የቤተሠቡ መተዳደርያ ጥሪት ነው..ወደድኩሽ ብሎ ለተጠጋት ባል ነኝ ብሎ እቤቷ ለአመታት ለኖረው ወርቅ አለማው አምናና አሳልፋ የሠጠችው።ወርቅ አለማው የምንትዋብ የበፊት ሟች ባል ተቀጣሪ ሰራተኛ ሁኖ ከአምሥት አመት በላይ የኖረ የ40 አመት ጎልማሳ ነው።ምንትዋብ ከእሡ ጋር የመቀራረብ እድሉ ያጋጠማት የልጇ አባት የሆኑት አዛውንት ባሏ ከሞቱ በሁዋላ በእሳቸው ይተዳደር የነበረውን ሆቴል እሷ መቆጣጠር ስትጀምር ነበር።ምክንያቱም ወርቅ አለማውም የሆቴሉ ስራ-አስኪያጅ ስለነበር በየቀኑ የመገናኘትና የመነጋገር እድል ነበራቸው።ሳያስቡት መቀራረብ ቀስ በቀስ
መሳሳብ ጀመሩ..
ትክክለኛውን ነገር ፈታተን እና ከፋፍለን እንየው ከተባለ ግን ሳያስቡት የሚለው ቃል የሚሠራው ለምንትዋብ ብቻ ነው...ወርቅ አለማው እያንዳንዷን እርምጃውን በእቅድ ነበር ያከናወናት...ቀድሞውንም በፍቅር ስም እየማለ የሚከውነው ከፍቅር ውጭ የሆነ አላማ ነበረው።በፍቅር መሠላልነት በመንጠላጠል ወደ ሀብት ማማ ላይ መንጠልጠል..አዎ ይሄን በልቡ ውስጥ በሚስጥር ቀብሮ ለማንም ትንፍሽ ሳይል በአላማ ሲንቀሳቀስ ነበር።...ያው ጥሩም ሆነ መጥፎ ነገር ሠው ብርቱና የአሸናፊ ሀይል በውስጡ ይዞ የሚዞር የእግዛብሔርን እስትንፋስ የተጋራ ልዩ ፍጡር ነውና ከልቡ ካቀደ..ያቀደውንም እንዲሳካለት ሳይሰለች ከጣረና ከለፋ ይሳካለታልና ይሄው ለሶስት አመት በማድባት ከሠራ በኋዋላ ዛሬ ያሳካው ይመስላል...ክፋቱ ይሄንን እግዛብሔር ከእስትንፋሱ ጋር ደባልቆ የሠጠውን የአሸናፊነት ሀይል በጎ ላልሆነ ነገር ስለተጠቀመበት(ተጠቅሞበት ከሆነ ማለቴ ነው)እንዴት ነው የሚቀጣው......? አዎ ምንትዋብ ዛሬ ነገሮች ከእጇ ሾልከው ያመለጡ ከመሠሉ በሁዋላ ነው አይኖቿ በድርበቡም ቢሆን የተከፈቱላት እና ልቦናዋም በጥርጣሬ ይታመሥ የጀመረው... ...እርግጥ አሁን ሥጋት ነው እንጂ ምንም የሚታወቅና የተረጋገጠ ነገር የለም።እውነት በውስጧ እንደጠረጠረሽው ከድቷት ይሆን ወይስ በሄደበት ሀገር አደጋ አጋጥሞት.. ...?ሌባ ዘርፎት ወይስ ሽፍታ ገድሎ አንድ ስርቻ ጥሎት? እግዜር ነው የሚያውቀው።ምንትዋብ ማለቂያ የሌላቸው ግትልትል ሀሳቦቿን በአእምሮዋ ስታመላልስ ቆይታ ድንገት እንደመባነን ብላ ወደ ቀልቧ ስትመለስ የ29 አመቱ ወጣት የፖሊስ መኮንን ልጇ ስሯ ተንበርክኮ አይን አይኗን በሀዘኔታ እያያት ትካዜዋን ሲጋራት ተመለከተች......
<<የኔ ውሻ>>አለችው እጇን ግንባሩ ላይ ጭና
<<አቤት እማ>>
<<የምሳ ሰአት ደርሶ ነው የመጣኸው? ምን አንበረከከህ ደግሞ..? ለምን አትነሳም?>>
<<አዎ 7 ሰአት ሊሆንኮ ነው...ጠዋት ትቼሽ የሄድኩበት ቦታ ሳገኝሽኮ ደነገጥኩ>> በማለት ከተንበረከከበት በመነሳት ከጎኗ ሶፋው ላይ ተቀመጠና መናገር ጀመረ
<<እማ ያንቺ ስጋት ሙሉ በሙሉ ግልፅ አልሆነልኝም..ለስራ ነው የወጣው አይደል...? ለዚያውም ጅቡቲ ድረስ...እርቀቱን አስቢው የቆየበትን ግዞኮ ያን ይህል ተስፋ የሚቆረጥበት አይደለም...ሶስት አራት ወር የሚቆይበት ጉዳይ ሊያጋጥመው ይችላል>>እናቱን ለማፅናናት ብሎ እንጂ ሰውዬው ያለምንም ነገር ድምጹን አጥፍቶ ይሄን ያህል ግዜ እንዳልቆየ የሱም ልብ ጠርጥሯል።
<<መቆየቱ አይደለም ያስጨነቀኝ።ባልተለመደ መልኩ ለአንድ ቀንም ቢሆን ያለመደወሉ...ስልኩም ጥሪ ያለመቀበሉ ነው ያሳሰበ ኝ....በቃ ውስጤ ፈርቷል ።>>አለችው ከአይኖቿ ያለፍላጎቷ የሚረግፈውን እንባ በእጆቿ እየጠራረገች
<<እርግጥ መደወል ነበረበት...ሳይመቸው ቀርቶ ይሆናል።ወይንም የሡ አለመደወል እኛን ይሄን ያህል ያስጨንቃቸዋል ብሎ ስላላሠበም ሊሆን ይችላል።>>
ምንትዋብ ከተቀመጠችበት ተነሳች...በአንድ እጇ ወገቧን ይዛ በሌላ እጆ የተንጨፈረረ ፀጉሯን ይበልጥ እንዲንጨፋረር እያፍተለተለች ንግግሯን ቀጠለች<<አዎ..እሡን እንኳን እውነትህን ነው..አጅሬ ምን ጎደለበት? እስቲ ተወኝ..ጉድ ሳያደርገኝ አልቀረም...በውስጤ እሳት እየተንቀለቀለ ነው።አሁን ትንሽ እረፍት ልውሰድ....>>ብላ እግሮቿን እየጎተተች ሳሎኑን ለቀቀችና ወደ መኝታ ቤቷ ሄደች።
ኮማንደር መሀሪ የእናቱን ወደ መኝታ ቤቷ ገብታ በራፉን ከውስጥ መቀርቀሯን ከተመለከተ በሁዋላ ከኪሱ ሞባይሉን አወጣና ደወለ...ፍቅረኛው ጋር።
የእናቱ ጭንቀት የሱም ጭንቀት ሆኗል...ከዚህ ጭንቀቱ ረገብ እንዲል ደግሞ ወደ ሥራ ከመግባት ይልቅ ፍቅረኛውን ማግኘት ይሻለዋል። ከአምስት ጥሪ በሁዋላ ስልኩ ተነሳ።ግን እሷ አልነበረችም ያነሳችው ታናሽ እህቷ ነበረች።
ሞባይሏን እቤት ጥላ እንደወጣችና እቤት እንደሌለች ነገረችው...ምንም አላላትም ስትመጣ እንድትደውልለት መልእክት አስቀምጦላት ስልኩን ዘጋው።
<<ይቺ ደግሞ ሲፈልጓት ሁሌ የማትገኝ ሰበበ ብዙ የሆነች የልብ በሽታ ነች>>ብስጭቱ ሳያስበው ድምጽ አውጥቶ እንዲነጫነጭ እስገደደው።ደግነቱ ሳሎኑ ውስጥ ለብቻው ስለሆነ የሰማው ሰው አልነበረም።
ምን ማድረግ እንዳለበት ባለማወቅና ግራ በመጋባት ክፍሉ ውስጥ መንጎራደድ ጀመረ ሁሉ ነገር አስጠላው።ይሄን ወርቅ አለማው የተባለውን አባቱ ከሞተ በሁዋላ የእናቱ ባል ሆኖ እቤታቸው ለሶስት አመት የኖረውን ሠውዬ ከመጀመርያው አንስቶ ቀልቡ ወዶትና ልቡም ተቀብሎት አያውቅም ነበር..ግን ለእናቱ ካለው ክብርና ፍቅር የተነሳ ከአንደበቱ ቃላት አውጥቶ ተቃውሞውን ገልጾ ወይም ፊቱን በማጨማደድ ያለመፈለግ ስሜቱን አሳውቆ አያውቅም ነበር...እንዴት ብሎ እናቱን<<እማዬ የእንጀራ አባቴን አልወደድኩትም..ጥሩ ባል አልመረጥሽም...ይቅርብሽ>>ሊላት ይችላል? በፍጹም እንደዛ ማድረግ አይቻለውም።አስተዳደጉም ያንን አይፈቅድለትም።በዚህ ምድር ላይ በጣም የሚያፈቅረውና በዛውም ልክ የሚፈራው ሰው ቢኖር እናቱን ነው።
ቢሆንም ግን ሁልግዜ አንድ ቀን አንድ ነገር እንደሚከሰት ይጠረጥር ነበር...አሁን ያ ጥርጣሬው በአስፈሪ መልኩ እውን ሳይሆን አልቀረም<<መሀሪ>>ከኪችን አከባቢ የመጣ የጥሪ ድምጽ ከሰመጠበት ሀሳብ ውስጥ መዞ አወጣው።መስታወት ነበረች።መስታወት የ25 አመት የጎመራች ወጣት ስትሆን በቤታቸው ከ12 አመት በላይ የኖረች ሠራተኛችው ነች...ለነገሩ እንዲሁ ስሙ ነው እንጂ ሠራተኛ ከማለት የማደጎ ልጃቸው ነች ማለት ይቀላል
👍10❤1
<<ምነው መስ ፈለግሽኝ?>>
አላት..ከተረጋጋ በሁዋላ
<<ምሳ ላቀርብልህ ነው>>
<<በቃኝ አሁን አልበላም>>
<<እንዴ ቁርስም በቃኝ ብለህ ሄድክ ምሳም በቃኝ..?እዚህ ቤትኮ ተመጋቢው እኔ ብቻ ሆንኩ።እትዬ ምንቴም ይሄው በሶስት ቀን አንዴ ብቻ ነው ምግብ ምታሸተው...አሁን አንተም ታከልክበት..እረ ለኔ ሞራል እንኳን ስትሉ ትንሽ ቅመሱ..>>
<<አሁን መብላት ስላላሠኘኝ ነው...ትንሽ ቆይቼ እበላለሁ...ይልቅ ምሳውን ተይና ጠዋት ሰው ፈልጎኝ ነበር እንዴ?>>ውስጡን እየበላው ያለውን ጥያቄ ጠየቃት
<<ማንም አልፈለገህም>>
<<የስልክ መልእክትም የለኝም?>>
<<ማንም አልደወለም>>አሁንም ተስፋ አልቆረጠም።
<<ሮዝም አልደወለችም?>>
የሮዝን ስም ስትሰማ ፊቷ በጥላቻ ተጨማደደ
<<እሷማ ደውላ ነበር መሰለኝ>>
<<እንዴት መሰለኝ?>>ሀይሉ ጠንከር ባለ ድምጽ ጠንከር ብሎ ጠየቃት
<<ደውላለች በቃ>>
<<ምን አለች?>>
<<ማታ ከተመቸኝ እመጣለሁ ብላለች...ላንተ ግን ባትመጣ ይሻልሀል>>
<<አልገባኝም.....?>>
<<ታውረህ መች ይገባኸል....ስለማፈቅርህ ቀንቼ እንዳይመስልህ...እርግጥ ከማንም ሴት ጋር ሳይህ ቅር ይለኛል ምክንያቱም ባትወደኝም እወድሀለሁ...ባታፈቅረኝም አፈቅርሀለሁ።በዚህም የተነሣ የኔ ብትሆንና ከሌላ ሴት ጋርም ባላይህ ደስ እንደሚለኝ አልደብቅህም...ግን ከሮዝ ጋር ሳይህ ደግሞ ይበልጥ እበሳጫለሁ...እሷ ፈጽሞ ለአንተ የምትሆን ሴት አይደለችም።>>
<<ለምን ቆንጆ አይደለችም....?>>
ፈገግ እያለ ጠየቃት
<<ቆንጆማ ቆንጆ ነች..ውብ ቆንጆ።ግን ያም ቢሆን አታፈቅርህም እያስመሠለች እንጂ ላንተ ያላት ፍቅር ጥልቀት የለውም።ነገረ ስራዋ ሁሉ ከአንገት በላይ ነው።ማፍቀርያዋ የተበላሸባት ሴት ትመስለኛለች።>>
<<እሙ ስለምክርሽ አመሠግናለሁ..ግን ሮዝን አላወቅሽያትም...እርግጠኛ ነኝ ወደፊት በደንብ ስትግባቡና በደንብ ስታውቅያት፤ይሄን ሀሣብሽን ትቀይሪያለሽ።
<<እሺ ይሁንልህ እኔ ግን ተናግሬያለሁ>>ብላው ፊቷን አዞረችና ወደ ኩሽናዋ ተመለሠች።
ኮማንደር መሀሪም በሀሳብ እየተብሠለሠለ ቤቱን ትቶ..ግቢውን ለቆ ወደ ሥራ ሄደ።እራሱን ሥራ ውስጥ ለመቅበር....የምናቡን ጫጫታ ለግዜውም ቢሆን ለማስታገስ።
💫ይቀጥላል💫
እንደተለመደው Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
አላት..ከተረጋጋ በሁዋላ
<<ምሳ ላቀርብልህ ነው>>
<<በቃኝ አሁን አልበላም>>
<<እንዴ ቁርስም በቃኝ ብለህ ሄድክ ምሳም በቃኝ..?እዚህ ቤትኮ ተመጋቢው እኔ ብቻ ሆንኩ።እትዬ ምንቴም ይሄው በሶስት ቀን አንዴ ብቻ ነው ምግብ ምታሸተው...አሁን አንተም ታከልክበት..እረ ለኔ ሞራል እንኳን ስትሉ ትንሽ ቅመሱ..>>
<<አሁን መብላት ስላላሠኘኝ ነው...ትንሽ ቆይቼ እበላለሁ...ይልቅ ምሳውን ተይና ጠዋት ሰው ፈልጎኝ ነበር እንዴ?>>ውስጡን እየበላው ያለውን ጥያቄ ጠየቃት
<<ማንም አልፈለገህም>>
<<የስልክ መልእክትም የለኝም?>>
<<ማንም አልደወለም>>አሁንም ተስፋ አልቆረጠም።
<<ሮዝም አልደወለችም?>>
የሮዝን ስም ስትሰማ ፊቷ በጥላቻ ተጨማደደ
<<እሷማ ደውላ ነበር መሰለኝ>>
<<እንዴት መሰለኝ?>>ሀይሉ ጠንከር ባለ ድምጽ ጠንከር ብሎ ጠየቃት
<<ደውላለች በቃ>>
<<ምን አለች?>>
<<ማታ ከተመቸኝ እመጣለሁ ብላለች...ላንተ ግን ባትመጣ ይሻልሀል>>
<<አልገባኝም.....?>>
<<ታውረህ መች ይገባኸል....ስለማፈቅርህ ቀንቼ እንዳይመስልህ...እርግጥ ከማንም ሴት ጋር ሳይህ ቅር ይለኛል ምክንያቱም ባትወደኝም እወድሀለሁ...ባታፈቅረኝም አፈቅርሀለሁ።በዚህም የተነሣ የኔ ብትሆንና ከሌላ ሴት ጋርም ባላይህ ደስ እንደሚለኝ አልደብቅህም...ግን ከሮዝ ጋር ሳይህ ደግሞ ይበልጥ እበሳጫለሁ...እሷ ፈጽሞ ለአንተ የምትሆን ሴት አይደለችም።>>
<<ለምን ቆንጆ አይደለችም....?>>
ፈገግ እያለ ጠየቃት
<<ቆንጆማ ቆንጆ ነች..ውብ ቆንጆ።ግን ያም ቢሆን አታፈቅርህም እያስመሠለች እንጂ ላንተ ያላት ፍቅር ጥልቀት የለውም።ነገረ ስራዋ ሁሉ ከአንገት በላይ ነው።ማፍቀርያዋ የተበላሸባት ሴት ትመስለኛለች።>>
<<እሙ ስለምክርሽ አመሠግናለሁ..ግን ሮዝን አላወቅሽያትም...እርግጠኛ ነኝ ወደፊት በደንብ ስትግባቡና በደንብ ስታውቅያት፤ይሄን ሀሣብሽን ትቀይሪያለሽ።
<<እሺ ይሁንልህ እኔ ግን ተናግሬያለሁ>>ብላው ፊቷን አዞረችና ወደ ኩሽናዋ ተመለሠች።
ኮማንደር መሀሪም በሀሳብ እየተብሠለሠለ ቤቱን ትቶ..ግቢውን ለቆ ወደ ሥራ ሄደ።እራሱን ሥራ ውስጥ ለመቅበር....የምናቡን ጫጫታ ለግዜውም ቢሆን ለማስታገስ።
💫ይቀጥላል💫
እንደተለመደው Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍2
#ብዙ_እያሳዘኑ_ብዙ_የሚያስቁ
"የማያውቁት ሀገር
አይናፍቅም የሚል ፣ ብዙ አላዋቂ
ማያውቃትን ሀገር ፣
"እወርሳለሁ " የሚል ፣ ገነትን ናፋቂ፡፡
************************
ሁለት እግር ይዞ..
ሁለት ዛፍ መውጣት ፣ የሚያምረው ዛፍ ቆራጭ
በመንታ መንገድ ላይ...
ለመጓዝ የሚወድ ፣ ብኩን መንገድ መራጭ ።
******************************
በኮት ላይ ኮት ለብሶ...
"ሁለት ኮት ያለው ፣
አንዱን ለሌለው ይስጥ" ፣ የሚል ደቀ መዝሙር
ከመንገድ ገፍትሮህ...
"እያየህ ሒድ " የሚል ፣
ማየትን የማያውቅ ፣ ደፋር አይነ ስውር።
***********-**-***********
"ዝምታ ወርቅ ነው"
እያለ ሚያወራ ፣ ብዙ ተናጋሪ
"እድል እድል " የሚል...
እድል የከዳችው ፣ የሎተሪ አዟሪ።
*****************************
አድር ባይ ክርክር...
ለፍቅር ተሟግቶ ፣ ለገንዘብ ሚጣላ
"አንድንድ ሰው የምላ..
አንድሰው የሞላ"
እያለ የሚጮህ ፣
ራሱን እንዳንድ ሰው ፣ ማይቆጥር ወያላ ።
**----------***************
"በፆም ስጋ አልበላም "፣ የምትል ዘማዊ
አሳ እያሰገረ...
"አሳ አትብሉ " ብሎ ፣ ሚጮህ ባህታዊ።
**********************-*******
ጠዋት ጠዋት መዝሙር ፣
ማታ ማታ ዘፈን ፣ ሚያሰማ ንግድ ቤት
ምንም የማይሰራ...
"አለሁ አለሁ " የሚል ፣ የሌለ መስሪያ ቤት።
*******************************
ገብቷችኀል" የሚል ...
እራሱ ያልገባው ፣ ሰነፍ አስተማሪ
"ገብቶናል" እያለ...
ፈተናውን ዜሮ ፣ ሚደፍን ተማሪ።
ሌላም
ሌላም
ሌላም ፣
ብዙ እውነት ነገር
ብዙ ውሸት ነገር
በበዙባት ሀገር
"ዝም በል" ሚል ይበዛል ፣ ምንም ሳትናገር፡፡
ሁሉም ያስቃሉ!!!
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
"የማያውቁት ሀገር
አይናፍቅም የሚል ፣ ብዙ አላዋቂ
ማያውቃትን ሀገር ፣
"እወርሳለሁ " የሚል ፣ ገነትን ናፋቂ፡፡
************************
ሁለት እግር ይዞ..
ሁለት ዛፍ መውጣት ፣ የሚያምረው ዛፍ ቆራጭ
በመንታ መንገድ ላይ...
ለመጓዝ የሚወድ ፣ ብኩን መንገድ መራጭ ።
******************************
በኮት ላይ ኮት ለብሶ...
"ሁለት ኮት ያለው ፣
አንዱን ለሌለው ይስጥ" ፣ የሚል ደቀ መዝሙር
ከመንገድ ገፍትሮህ...
"እያየህ ሒድ " የሚል ፣
ማየትን የማያውቅ ፣ ደፋር አይነ ስውር።
***********-**-***********
"ዝምታ ወርቅ ነው"
እያለ ሚያወራ ፣ ብዙ ተናጋሪ
"እድል እድል " የሚል...
እድል የከዳችው ፣ የሎተሪ አዟሪ።
*****************************
አድር ባይ ክርክር...
ለፍቅር ተሟግቶ ፣ ለገንዘብ ሚጣላ
"አንድንድ ሰው የምላ..
አንድሰው የሞላ"
እያለ የሚጮህ ፣
ራሱን እንዳንድ ሰው ፣ ማይቆጥር ወያላ ።
**----------***************
"በፆም ስጋ አልበላም "፣ የምትል ዘማዊ
አሳ እያሰገረ...
"አሳ አትብሉ " ብሎ ፣ ሚጮህ ባህታዊ።
**********************-*******
ጠዋት ጠዋት መዝሙር ፣
ማታ ማታ ዘፈን ፣ ሚያሰማ ንግድ ቤት
ምንም የማይሰራ...
"አለሁ አለሁ " የሚል ፣ የሌለ መስሪያ ቤት።
*******************************
ገብቷችኀል" የሚል ...
እራሱ ያልገባው ፣ ሰነፍ አስተማሪ
"ገብቶናል" እያለ...
ፈተናውን ዜሮ ፣ ሚደፍን ተማሪ።
ሌላም
ሌላም
ሌላም ፣
ብዙ እውነት ነገር
ብዙ ውሸት ነገር
በበዙባት ሀገር
"ዝም በል" ሚል ይበዛል ፣ ምንም ሳትናገር፡፡
ሁሉም ያስቃሉ!!!
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ሁለት
:
✍ደራሲ-በዘረሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...ኩማንደር መሀሪ ቢሮው ቁጭ ብሎ ሰሞኑን በእጁ የገቡትን የክስ ፋይሎች እያገላበጠ ነው፡፡ግን አዕምሮው ተረጋቶ የነገሮችን ብልት መከፋፈል እና መመርመር አልተቻለውም፡፡የቤተሰቡ ጉዳይ በመሀል ጣልቃ እየገባበት እየረበሸው ነው፡፡ያለችው አንድ እናቱ ብቻ ስለሆነች እና አንድ አይን ያለው በእሳት አይጫወትም እንደሚባለው የእሱም እናት ሙሉ ቤተሰቡ ማለት ነች፤ የእሷ በሀሳብ መናወዝ እሱን እያናወዘው ነው፤የእሷ ያለመረጋጋት እሱንም ልቦናውን እያተረማመሰው ነው፡፡እያገላበጠ የነበረውን የክስ የወንጀል ሪፖርት ዶሴ መልሶ ከደነውና የእናቱ ጉዳይ ላይ ብቻ አተኮረ፡፡
‹‹ወይ ጉድ ምን አይነት አውሬ ሰውዬ ነው ››ሲል ስለወርቅአለማው አሰበ፡፡ወርቅ አለማው ከቤት ከወጣ ሶስተኛ ወሩን እያገመሰ ነው፡፡እናትዬው በአስቸኳይ ወርቅአለማው የሚባለውን ሰውዬ በተመለከተ የሆነ ነገር ካልሳማች በቃ ይለይላታል ፤ጨርቋን ጥላ ማበዶ የማያጠራጥር ሀቅ ነው፡፡ስለዚህ ማድረግ ስላለበት ጉዳይ ሲያሰላስል የሆነ ሀሳብ መጣለት ፡፡ሞባይሉን አወጣና ጓደኛው ጋር ደወለ..ኮማንደር ደረስ ጋር
‹‹ሄሎ››
‹‹የት ነህ?››
‹‹ከተማ ነኝ..ምነው በሰላም››
‹‹ለግል ጉዳዬ ፈልጌህ ነበር››
‹‹እ በቃ ገባኝ..››
‹‹ምኑ ነው የገባህ?››
‹‹ያው ተዘጋጅ ልትለኝ አይደል..››
‹‹ለምኑ ነው የምዘጋጀው.?.››
‹‹አንደኛ ሚዜ እንድሆንህ ነዋ ፡፡መቼስ ከእኔ የቀረበ ጓደኛ የለህም..ሮዝን ልታጋባ በመሆኑ አንደኛ ሚዜ እንድሆንህ ቀድመህ ማሳሰብ ጥሩ ነው..መቼስ በዛሬ ጊዜ ሚዜ መሆን ጣጣውም ወጪው አይጣል ነው..እስቲ እንሞክራለን ፡፡መቼስ እምቢ አይባል ነገር››አለው ኩማንደር ደረሰ፡፡
ምንም ይሁን ምንም በማንኛውም ነገር እንደቀለደ ነው፡፡ለእሱ ህይወት ዘና የሚሉባት በፈገግታ የሚስተናገዱባት ብርሀናዊ ስፍራ ነች ፡፡ከመሀሪ ጋር የጠበቀ ጓደኝነት በመሀከላቸው ቢኖርም በባህሪ ግን ምንም ሚያመሳስላቸው ነገር የለም፡፡ደረሰ ቀልድ ወዳጅ፤ ሁልጊዜ ፊቱ በፈገግታ የተሞላ ፤ለስራው ብዙ ግድ የሌለው ፤ተጨማሪ ገንዘብ የሚያስገኝ ስራ እስከአልሆነ ድረስ ተረጋግቶ ሲሞላለት ብቻ የሚሰራ ሰው ነው፡፡መሀሪ ደግሞ በተቃራኒው ለዋዛ ፈዛዛ ብዙም ግድ የሌለው፤የተቋጠረ ፊት ባለቤት የሆነ፤ ስራውን አክባሪ ፤የሞያውን ስነምግባር አክብሮ የሚንቀሳቀስ ሰው ነው፡፡እንደዛም ሆኖ ጓደኛሞች ናቸው፡፡
‹‹ባክህ አትዘባርቅ ለቁም ነገር ነው የደወልኩልህ››ኮስተር አለበት፡፡
‹‹ቀጥላ ምን ያነጫንጭሀል››
‹‹ባክህ ያ በቀደም ያጫወትኩህ የእናቴን ጉዳይ እየተባባሰ ነው››
‹‹ምነው አባትህ አልደወለም እንዴ?››
‹‹አባትህ አልከኝ..››አለው በጣም የሚጠላው ሰው አባቱ ሆኖ መጠቀሱ ቅረ አሰኝቶት
‹‹ያው ነው እናቴን ያገባ ሁሉ አባቴ ነው ሲባል አልሰማህም››
‹‹ይሁንልህ ..እስከዛሬ ድረስ ምንም ድምጹ የለም ፤እሷ ደግሞ ከእለት ወደእለት በሀሳብ እያለቀች ነው…. ምግብ መመገብ ካቋመች ሰነበተች ..››
‹‹እና ምን እንድናደርግ ፈለግክ?››
‹‹የእሱ ጓደኛ ነኝ ብለህ እንድትደውልላት እና ለጊዜውም ቢሆን እንድትጽናናት ነው፡፡ የሚያረጋጋትን የሆነ ነገር እንድትነግራት ፈልጌ ነበር››
‹‹ማ እኔ?››
‹‹አዎ አንተ››
‹‹አሁን ልደውል››
‹‹አይ ያንተ ነገር… ለሁሉ ነገር መጣደፍ ትወዳህ፡፡ በደንብ አስብበትና ምን ማለት እንዳለብህ ተጠንቅቀህ ዛሬ ማታ ወይም ነገ ትደውላለህ››
‹‹እሺ እንዳልክ ››
‹‹እሺ ቻው››ተሰናብቶት ስልኩን ዘጋው፡፡
ወደተከፈቱት ዶሴዎች ሊመለስ ቢሞክርም አልተሳካለትም፡፡ ከሞባይሉ ላይ ሰዓቱን ተመለከተ፡፡10 ሰዓት ነው፡፡ በዚህን ሰዓት ከቢሮ ወጥቶ መሄድ አልፈለገም ፡፡ደግሞስ የት ይሄዳል… ?ሮዛ እንደሆነ እንኳን ያለቀጠሮ በቀጠሮም በመከራ ነው የምትገኝለት..፡፡ስለሚያፈቅራት እንጂ ይሄ ሁኔታዎ በጣም አማሮታል፡፡በዛ ላይ በከተማው ውስጥ እንኳን በሳምንት ከሁለት ወይ ከሶስት ቀን በላይ አትገኝም ፡፡ዛሬ ቦረና ሄጃለው ትለዋለች..በማግስቱ ደግሞ ሀዋሳ ትሆናለች ፡፡በዚህ ጉዳይ ብዙ ጊዜ የመረረ ጠብ ውስጥ ገብተዋል፡፡እሷ ግን ከእለት እለት እየባሰባት እንጂ ልትሻሸል አልቻለችም፡፡
አንዴ ያግባት እንጂ ይሄንን ከቦታ ቦታ ለመዘዋወር ሰበብ እየሆናት ያለውን ያየር ባየር ንግድ ያስተዋትና እዛው ዲላ ከታማ ውስጥ አንድ ቡቲክ ከፍቶላት የተረጋጋ ስራ እየሰራች የተረጋጋ ኑሮ እንድትኖር ያደርጋታል..በዛ ውስጥ እሱም በደንብ ይረጋጋል..አዎ ይህ ነው ዕቅዱ ፡፡ እንደእዛ ካደረገ እንደልቡ በፈለገ ጊዜ ያገኛታል፡፡እንደዚህ አይራባትም፡፡ይሄ የእሱ ሀሳብ ነው፡፡ ሀሳብማ ከዚህም የጠከረ ነው፡፡ሮዝን ሊያገባት የሚፈልገው በኦርቶዶክስ ሀይማኖት የጋብቻ ስርአት መሰረት ነው፡፡በተክሊል፡፡ይሄም እንዲሆን የፈለገበት ምክንያት ለአስር አመት በዲቁንና ባገለገለበት ቤተክርስቲያን መዳርና ለሌሎችም ታናናሾቹ ምሳሌ መሆን ስለሚፈልግ ነው፡፡እራሱንም ማስደሰት ለፈጣሪ ያለው ክብር እና ታማኝነትም ማረጋገጥ ስለሚፈልግ ነው፡፡
ደግሞም የሟች አባቱ ምኞትም እንደዛ ነበር፡፡ለዚህም ሲል ከሮዝ ጋር ከአንድ አመት በላይ በፍቀርኝነት ቢያሳልፉም ጾታዊ ግንኙነት ግን አልፈፀሙም.. በዚህም የተነሳ እሱ ድንግል እንደሆነ ሁሉ እሷም ድንግል እንደሆነች በሙሉ ልቡ ያምናል…እርግጥ ዝም ብሎ አይደለም ያመናት ሲጠይቃት ወንድ አላውቅም ስላለችው ነው፡፡የሚያየውን እንቅስቃሴዋን እና ተግባሮን ሳይሆን አንደበቷን አመነ…ሚገርመው ግን ሮዝ ወሲብ ከጀመረች አስራ ሶስት አመታት አልፎታል፡፡ገና ደረቷ ላይ ያሉ ጡቷቾ ለአይን ሳይሞሉ..ብልቷ በስርአት ፀጉር አብቅሎ ሳይወጣለት ነው የጀመረችው፡፡እርግጥ አጀማመሮ ከእሷ ፍላጐትም ቁጥጥርም ውጭ በሆነ ሁኔታ እና አጋጣሚ ነበር..፡፡ቢሆንም የረጅም ዓመት ልምድ አላት፡፡ለዛውም የጠነከረ ልምድ፡፡በዛ ላይ መሀሪን ፈጽሞ አታፈቅረውም፡፡የቀረበችው ለጥቅም ነው፡፡ከቦረና እና ከኬኒያ ወደ መሀል ሀገር ለምታሻግራቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ከለላ እንዲሆናት ፡፡እሱ በቀጥታ ባይረዳት እንኳን በእሱ አማካኝነት በምትተዋወቃቸው ሰዎችም ለመጠቀም እንጂ እሷ በምንም አይነት የአንድ ሰው ፍቅረኛ ሆና መታሰር የምትችል ሴት አይደለችም፡፡
በአሁኑ ጊዜ እንኳን ቦረና 3 ፤ሀዋሳ 2 ፤ሻሸመኔ 2 እዚሁ ዲላ እንኳን እንድ በወሲብ የምትወዳጃቸው ጓደኖች አሏት፡፡በዛ ላይ ከወንድ ጋር ባለት የየእለት ግንኙነት የትኛውንም ቀልቧን የሳበትን ወንድ ሳታገኘውና ሳትጠቀምበት ማባከን አትፈልግም፡፡የእዚህ ጉዳይ መጨረሻው ወይም የግንኙነታቸው ማገባደጃው ምን እንደሚሆን ለሚያስበው የቅርብ ሰው ሁሉ ይጨንቃል፡፡ኩማደሩ ግን ለጊዜው ስለእሷ ከሚያውቀው ይልቅ የማያውቀው በብዙ ሺ እጥፍ ስለሚበልጥ በሁኔታው እየተጨነቀ አይደለም፡፡ለምሳሌ እሱ እህቷ ነች ብሎ የሚያስባት እቤታቸው ሲሄደ የሚገኛት የ12 ዓመቷ ሄለን የእሷ የልጅነት ልጇ የአብራኮ ክፋይ እንደሆነች ምንም ፍንጭ የለውም፡፡ለጊዜው እሱን የሚያስጨንቀው ቀላሉ ነገር ነው ፡፡በፈለጋት ጊዜ እያገኛት ስላልሆነ ብቻ ያንን ማስተካከል እና እንዴት እና መቼ እንደሚያገባት ማሰብ ..በቃ፡፡
….ግን ስለእሷ ያልሰማቸውን ሲሰማ ያማያውቃአቸውን ሲያውቅ ምን ይፈጠር ይሆን..?ጊዜ የሚመልሳቸው የነገ ስጋቶች ናቸው፡፡
ሀሳቡን ከእሷም መለሰና በአይኑን ከጀርባው ወዳለው ሼልፍ ወረወረ፡፡ አንድ 10 የሚሆኑ በወንጀል እና በህግ ላይ የሚያወሩ መጽሀፎች ይገኛሉ ፡፡አንድን አንሳላና ገለጥ ገለጥ እያደረገ ማንበብ ጀመረ፡፡ከ15 ደቂቃ ቡኃላ
:
#ክፍል_ሁለት
:
✍ደራሲ-በዘረሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...ኩማንደር መሀሪ ቢሮው ቁጭ ብሎ ሰሞኑን በእጁ የገቡትን የክስ ፋይሎች እያገላበጠ ነው፡፡ግን አዕምሮው ተረጋቶ የነገሮችን ብልት መከፋፈል እና መመርመር አልተቻለውም፡፡የቤተሰቡ ጉዳይ በመሀል ጣልቃ እየገባበት እየረበሸው ነው፡፡ያለችው አንድ እናቱ ብቻ ስለሆነች እና አንድ አይን ያለው በእሳት አይጫወትም እንደሚባለው የእሱም እናት ሙሉ ቤተሰቡ ማለት ነች፤ የእሷ በሀሳብ መናወዝ እሱን እያናወዘው ነው፤የእሷ ያለመረጋጋት እሱንም ልቦናውን እያተረማመሰው ነው፡፡እያገላበጠ የነበረውን የክስ የወንጀል ሪፖርት ዶሴ መልሶ ከደነውና የእናቱ ጉዳይ ላይ ብቻ አተኮረ፡፡
‹‹ወይ ጉድ ምን አይነት አውሬ ሰውዬ ነው ››ሲል ስለወርቅአለማው አሰበ፡፡ወርቅ አለማው ከቤት ከወጣ ሶስተኛ ወሩን እያገመሰ ነው፡፡እናትዬው በአስቸኳይ ወርቅአለማው የሚባለውን ሰውዬ በተመለከተ የሆነ ነገር ካልሳማች በቃ ይለይላታል ፤ጨርቋን ጥላ ማበዶ የማያጠራጥር ሀቅ ነው፡፡ስለዚህ ማድረግ ስላለበት ጉዳይ ሲያሰላስል የሆነ ሀሳብ መጣለት ፡፡ሞባይሉን አወጣና ጓደኛው ጋር ደወለ..ኮማንደር ደረስ ጋር
‹‹ሄሎ››
‹‹የት ነህ?››
‹‹ከተማ ነኝ..ምነው በሰላም››
‹‹ለግል ጉዳዬ ፈልጌህ ነበር››
‹‹እ በቃ ገባኝ..››
‹‹ምኑ ነው የገባህ?››
‹‹ያው ተዘጋጅ ልትለኝ አይደል..››
‹‹ለምኑ ነው የምዘጋጀው.?.››
‹‹አንደኛ ሚዜ እንድሆንህ ነዋ ፡፡መቼስ ከእኔ የቀረበ ጓደኛ የለህም..ሮዝን ልታጋባ በመሆኑ አንደኛ ሚዜ እንድሆንህ ቀድመህ ማሳሰብ ጥሩ ነው..መቼስ በዛሬ ጊዜ ሚዜ መሆን ጣጣውም ወጪው አይጣል ነው..እስቲ እንሞክራለን ፡፡መቼስ እምቢ አይባል ነገር››አለው ኩማንደር ደረሰ፡፡
ምንም ይሁን ምንም በማንኛውም ነገር እንደቀለደ ነው፡፡ለእሱ ህይወት ዘና የሚሉባት በፈገግታ የሚስተናገዱባት ብርሀናዊ ስፍራ ነች ፡፡ከመሀሪ ጋር የጠበቀ ጓደኝነት በመሀከላቸው ቢኖርም በባህሪ ግን ምንም ሚያመሳስላቸው ነገር የለም፡፡ደረሰ ቀልድ ወዳጅ፤ ሁልጊዜ ፊቱ በፈገግታ የተሞላ ፤ለስራው ብዙ ግድ የሌለው ፤ተጨማሪ ገንዘብ የሚያስገኝ ስራ እስከአልሆነ ድረስ ተረጋግቶ ሲሞላለት ብቻ የሚሰራ ሰው ነው፡፡መሀሪ ደግሞ በተቃራኒው ለዋዛ ፈዛዛ ብዙም ግድ የሌለው፤የተቋጠረ ፊት ባለቤት የሆነ፤ ስራውን አክባሪ ፤የሞያውን ስነምግባር አክብሮ የሚንቀሳቀስ ሰው ነው፡፡እንደዛም ሆኖ ጓደኛሞች ናቸው፡፡
‹‹ባክህ አትዘባርቅ ለቁም ነገር ነው የደወልኩልህ››ኮስተር አለበት፡፡
‹‹ቀጥላ ምን ያነጫንጭሀል››
‹‹ባክህ ያ በቀደም ያጫወትኩህ የእናቴን ጉዳይ እየተባባሰ ነው››
‹‹ምነው አባትህ አልደወለም እንዴ?››
‹‹አባትህ አልከኝ..››አለው በጣም የሚጠላው ሰው አባቱ ሆኖ መጠቀሱ ቅረ አሰኝቶት
‹‹ያው ነው እናቴን ያገባ ሁሉ አባቴ ነው ሲባል አልሰማህም››
‹‹ይሁንልህ ..እስከዛሬ ድረስ ምንም ድምጹ የለም ፤እሷ ደግሞ ከእለት ወደእለት በሀሳብ እያለቀች ነው…. ምግብ መመገብ ካቋመች ሰነበተች ..››
‹‹እና ምን እንድናደርግ ፈለግክ?››
‹‹የእሱ ጓደኛ ነኝ ብለህ እንድትደውልላት እና ለጊዜውም ቢሆን እንድትጽናናት ነው፡፡ የሚያረጋጋትን የሆነ ነገር እንድትነግራት ፈልጌ ነበር››
‹‹ማ እኔ?››
‹‹አዎ አንተ››
‹‹አሁን ልደውል››
‹‹አይ ያንተ ነገር… ለሁሉ ነገር መጣደፍ ትወዳህ፡፡ በደንብ አስብበትና ምን ማለት እንዳለብህ ተጠንቅቀህ ዛሬ ማታ ወይም ነገ ትደውላለህ››
‹‹እሺ እንዳልክ ››
‹‹እሺ ቻው››ተሰናብቶት ስልኩን ዘጋው፡፡
ወደተከፈቱት ዶሴዎች ሊመለስ ቢሞክርም አልተሳካለትም፡፡ ከሞባይሉ ላይ ሰዓቱን ተመለከተ፡፡10 ሰዓት ነው፡፡ በዚህን ሰዓት ከቢሮ ወጥቶ መሄድ አልፈለገም ፡፡ደግሞስ የት ይሄዳል… ?ሮዛ እንደሆነ እንኳን ያለቀጠሮ በቀጠሮም በመከራ ነው የምትገኝለት..፡፡ስለሚያፈቅራት እንጂ ይሄ ሁኔታዎ በጣም አማሮታል፡፡በዛ ላይ በከተማው ውስጥ እንኳን በሳምንት ከሁለት ወይ ከሶስት ቀን በላይ አትገኝም ፡፡ዛሬ ቦረና ሄጃለው ትለዋለች..በማግስቱ ደግሞ ሀዋሳ ትሆናለች ፡፡በዚህ ጉዳይ ብዙ ጊዜ የመረረ ጠብ ውስጥ ገብተዋል፡፡እሷ ግን ከእለት እለት እየባሰባት እንጂ ልትሻሸል አልቻለችም፡፡
አንዴ ያግባት እንጂ ይሄንን ከቦታ ቦታ ለመዘዋወር ሰበብ እየሆናት ያለውን ያየር ባየር ንግድ ያስተዋትና እዛው ዲላ ከታማ ውስጥ አንድ ቡቲክ ከፍቶላት የተረጋጋ ስራ እየሰራች የተረጋጋ ኑሮ እንድትኖር ያደርጋታል..በዛ ውስጥ እሱም በደንብ ይረጋጋል..አዎ ይህ ነው ዕቅዱ ፡፡ እንደእዛ ካደረገ እንደልቡ በፈለገ ጊዜ ያገኛታል፡፡እንደዚህ አይራባትም፡፡ይሄ የእሱ ሀሳብ ነው፡፡ ሀሳብማ ከዚህም የጠከረ ነው፡፡ሮዝን ሊያገባት የሚፈልገው በኦርቶዶክስ ሀይማኖት የጋብቻ ስርአት መሰረት ነው፡፡በተክሊል፡፡ይሄም እንዲሆን የፈለገበት ምክንያት ለአስር አመት በዲቁንና ባገለገለበት ቤተክርስቲያን መዳርና ለሌሎችም ታናናሾቹ ምሳሌ መሆን ስለሚፈልግ ነው፡፡እራሱንም ማስደሰት ለፈጣሪ ያለው ክብር እና ታማኝነትም ማረጋገጥ ስለሚፈልግ ነው፡፡
ደግሞም የሟች አባቱ ምኞትም እንደዛ ነበር፡፡ለዚህም ሲል ከሮዝ ጋር ከአንድ አመት በላይ በፍቀርኝነት ቢያሳልፉም ጾታዊ ግንኙነት ግን አልፈፀሙም.. በዚህም የተነሳ እሱ ድንግል እንደሆነ ሁሉ እሷም ድንግል እንደሆነች በሙሉ ልቡ ያምናል…እርግጥ ዝም ብሎ አይደለም ያመናት ሲጠይቃት ወንድ አላውቅም ስላለችው ነው፡፡የሚያየውን እንቅስቃሴዋን እና ተግባሮን ሳይሆን አንደበቷን አመነ…ሚገርመው ግን ሮዝ ወሲብ ከጀመረች አስራ ሶስት አመታት አልፎታል፡፡ገና ደረቷ ላይ ያሉ ጡቷቾ ለአይን ሳይሞሉ..ብልቷ በስርአት ፀጉር አብቅሎ ሳይወጣለት ነው የጀመረችው፡፡እርግጥ አጀማመሮ ከእሷ ፍላጐትም ቁጥጥርም ውጭ በሆነ ሁኔታ እና አጋጣሚ ነበር..፡፡ቢሆንም የረጅም ዓመት ልምድ አላት፡፡ለዛውም የጠነከረ ልምድ፡፡በዛ ላይ መሀሪን ፈጽሞ አታፈቅረውም፡፡የቀረበችው ለጥቅም ነው፡፡ከቦረና እና ከኬኒያ ወደ መሀል ሀገር ለምታሻግራቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ከለላ እንዲሆናት ፡፡እሱ በቀጥታ ባይረዳት እንኳን በእሱ አማካኝነት በምትተዋወቃቸው ሰዎችም ለመጠቀም እንጂ እሷ በምንም አይነት የአንድ ሰው ፍቅረኛ ሆና መታሰር የምትችል ሴት አይደለችም፡፡
በአሁኑ ጊዜ እንኳን ቦረና 3 ፤ሀዋሳ 2 ፤ሻሸመኔ 2 እዚሁ ዲላ እንኳን እንድ በወሲብ የምትወዳጃቸው ጓደኖች አሏት፡፡በዛ ላይ ከወንድ ጋር ባለት የየእለት ግንኙነት የትኛውንም ቀልቧን የሳበትን ወንድ ሳታገኘውና ሳትጠቀምበት ማባከን አትፈልግም፡፡የእዚህ ጉዳይ መጨረሻው ወይም የግንኙነታቸው ማገባደጃው ምን እንደሚሆን ለሚያስበው የቅርብ ሰው ሁሉ ይጨንቃል፡፡ኩማደሩ ግን ለጊዜው ስለእሷ ከሚያውቀው ይልቅ የማያውቀው በብዙ ሺ እጥፍ ስለሚበልጥ በሁኔታው እየተጨነቀ አይደለም፡፡ለምሳሌ እሱ እህቷ ነች ብሎ የሚያስባት እቤታቸው ሲሄደ የሚገኛት የ12 ዓመቷ ሄለን የእሷ የልጅነት ልጇ የአብራኮ ክፋይ እንደሆነች ምንም ፍንጭ የለውም፡፡ለጊዜው እሱን የሚያስጨንቀው ቀላሉ ነገር ነው ፡፡በፈለጋት ጊዜ እያገኛት ስላልሆነ ብቻ ያንን ማስተካከል እና እንዴት እና መቼ እንደሚያገባት ማሰብ ..በቃ፡፡
….ግን ስለእሷ ያልሰማቸውን ሲሰማ ያማያውቃአቸውን ሲያውቅ ምን ይፈጠር ይሆን..?ጊዜ የሚመልሳቸው የነገ ስጋቶች ናቸው፡፡
ሀሳቡን ከእሷም መለሰና በአይኑን ከጀርባው ወዳለው ሼልፍ ወረወረ፡፡ አንድ 10 የሚሆኑ በወንጀል እና በህግ ላይ የሚያወሩ መጽሀፎች ይገኛሉ ፡፡አንድን አንሳላና ገለጥ ገለጥ እያደረገ ማንበብ ጀመረ፡፡ከ15 ደቂቃ ቡኃላ
👍5❤3
የቢሮ በራፍ ተንኰኰ
‹‹ይግቡ ክፍት ነው››
በራፉ ተከፍቶ ወደውስጥ የገባው ያልጠበቀው ሰው ነው‹‹እንዴ አንተው ነህ እንዴ በስርአት ምታንኳኳው.?ደግሞ አሁን ከተማ ነኝ አላልከኝም ነበር ?››
‹‹ባክህ ሚገርም ነገር ገጥሞኝ ነው ወደእዚህ የመጣውት..››እያለ ወደውስጥ ዘልቆ ገባና ወንበር ስቦ ከፊት ለፊቱ ተቀመጠ
‹‹የምን የሚገርም ነገር…?ደግሞ የምን ቦርሳ ነው የያዝከው ….?››
‹‹ባክህ አንድ ሚሊዬን ብር ነው››ብሎ በብስጭት ጠረጲዛው ላይ ወረወረለት
‹‹የምን ሚሊዬን ብር ..አንተ እኮ አታደርገም አይባልም.. ይሄን ያህል ብር ጉቦ ተቀበልኩ እንዳትለኝ››
‹‹ቢሆንማ በምን እድሌ..ደግሞ ጥሬ ብር እንዳይመስልህ ሀሽሽ ነው፡፡የሆኑ ሁለት ጐረምሶች ከሻሸመኔ ይመስለኛል ወደ ኬኒያ ሊያሻግሩ ሲሉ ነው ሲንከረፈፉ የተያዙተ››
‹‹ታዲያ እነሱ ለተያዙት አንተ ምን አበሳጨህ››
‹‹ለምን አልበሳጭ አንድ ሚሊዬን ብር እንደዋዛ እዲቃጠል ሲያደርጉ››
‹‹ለመሆኑ አንተ ነህ ያያዝካቸው?››እሱ እንዳላያዛቸው ያውቃል፡፡እንደዛ ሆኖ ቢሆን ኖሮ እዚህ አያደርሳቸውም ነበር ፡፡እዛው ተደራድሮ እዛው የድርሻው ተቀብሎ ጥፉ ከፊቴ ነበር የሚላቸው
‹‹ባክህ እኔ አይደለውም …አንድ ከርፋፋ 50 ሃለቃ ነው፡፡››
‹‹እና ታዲያ ምን ወደእኔ ቢሮ አመጣህ? ››
‹‹ይሄ ዕቃ አንተ ጋር እንዲቀመጥ ነው?››
‹‹ለምን ቢባል?››
‹‹የእኔ ሎከር አስተማማኝ አይደለም ቁልፍ የለውም ..››
‹‹እንዴ ለምን ኤግዚቢት ክፍል አታስርክበውም››
‹‹እሱንማ መች አጣውት ..ግን ሰውዬው ቆልፎ ልጄ ታሞብኛል ብሎ ወጥቷል አሉ እስከ ነገ ጥዋት አንተ ጋር ይቀመጥ፡፡››
‹‹ካልክ እሺ አለና ከመቀመጫው ተነሳና ሎከሩን ከፍቶ የሰጠውን ቦርሳ አስገባና ቆልፎበት፡፡ ቁልፉን ኪሱ ከተተና ቢሮውንም ቆልፈው ተያይዘው ወጡ፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like👍👍 በጣም እየቀነሰ ነው ምንድን ነው ታሪኩ አልተመቻችሁም ? እስቲ የቸመቻቹ 👍 Like እያደረጋቹ አስተያየት ያላችሁ እታች ባለው አድራሻ አድርሱኝ።
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
‹‹ይግቡ ክፍት ነው››
በራፉ ተከፍቶ ወደውስጥ የገባው ያልጠበቀው ሰው ነው‹‹እንዴ አንተው ነህ እንዴ በስርአት ምታንኳኳው.?ደግሞ አሁን ከተማ ነኝ አላልከኝም ነበር ?››
‹‹ባክህ ሚገርም ነገር ገጥሞኝ ነው ወደእዚህ የመጣውት..››እያለ ወደውስጥ ዘልቆ ገባና ወንበር ስቦ ከፊት ለፊቱ ተቀመጠ
‹‹የምን የሚገርም ነገር…?ደግሞ የምን ቦርሳ ነው የያዝከው ….?››
‹‹ባክህ አንድ ሚሊዬን ብር ነው››ብሎ በብስጭት ጠረጲዛው ላይ ወረወረለት
‹‹የምን ሚሊዬን ብር ..አንተ እኮ አታደርገም አይባልም.. ይሄን ያህል ብር ጉቦ ተቀበልኩ እንዳትለኝ››
‹‹ቢሆንማ በምን እድሌ..ደግሞ ጥሬ ብር እንዳይመስልህ ሀሽሽ ነው፡፡የሆኑ ሁለት ጐረምሶች ከሻሸመኔ ይመስለኛል ወደ ኬኒያ ሊያሻግሩ ሲሉ ነው ሲንከረፈፉ የተያዙተ››
‹‹ታዲያ እነሱ ለተያዙት አንተ ምን አበሳጨህ››
‹‹ለምን አልበሳጭ አንድ ሚሊዬን ብር እንደዋዛ እዲቃጠል ሲያደርጉ››
‹‹ለመሆኑ አንተ ነህ ያያዝካቸው?››እሱ እንዳላያዛቸው ያውቃል፡፡እንደዛ ሆኖ ቢሆን ኖሮ እዚህ አያደርሳቸውም ነበር ፡፡እዛው ተደራድሮ እዛው የድርሻው ተቀብሎ ጥፉ ከፊቴ ነበር የሚላቸው
‹‹ባክህ እኔ አይደለውም …አንድ ከርፋፋ 50 ሃለቃ ነው፡፡››
‹‹እና ታዲያ ምን ወደእኔ ቢሮ አመጣህ? ››
‹‹ይሄ ዕቃ አንተ ጋር እንዲቀመጥ ነው?››
‹‹ለምን ቢባል?››
‹‹የእኔ ሎከር አስተማማኝ አይደለም ቁልፍ የለውም ..››
‹‹እንዴ ለምን ኤግዚቢት ክፍል አታስርክበውም››
‹‹እሱንማ መች አጣውት ..ግን ሰውዬው ቆልፎ ልጄ ታሞብኛል ብሎ ወጥቷል አሉ እስከ ነገ ጥዋት አንተ ጋር ይቀመጥ፡፡››
‹‹ካልክ እሺ አለና ከመቀመጫው ተነሳና ሎከሩን ከፍቶ የሰጠውን ቦርሳ አስገባና ቆልፎበት፡፡ ቁልፉን ኪሱ ከተተና ቢሮውንም ቆልፈው ተያይዘው ወጡ፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like👍👍 በጣም እየቀነሰ ነው ምንድን ነው ታሪኩ አልተመቻችሁም ? እስቲ የቸመቻቹ 👍 Like እያደረጋቹ አስተያየት ያላችሁ እታች ባለው አድራሻ አድርሱኝ።
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3❤1
#የተቃጠለ_ልብ
:
#ክፍል_ሶስት
:
✍ደራሲ-በዘረሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...አየሩ ቀዝቃዛ ሲሆን ለሊቱ ደግሞ ፀጥታ ያረበበበት ነው፡፡ምንትዋብ አልጋዋ ላይ ተዘርራ አይኖን ጣሪያ ላይ ሰክታ ታስባለች፡፡ምሽቱም ገፍቶ 7 ሰዓት ማለፉን ግድግዳው ላይ የተንጠጠለውን የወርቅ ቅብ የግድግዳ ሰዓት ይናገራል፡፡እንደ ድሮ ቢሆን ለምንትዋብ ይሄ ጥሩ የእንቅልፍ ሰዓት ነበር ፡፡አሁን ግን ታሪክ ተቀይሯል፡፡ እንቅልፍ ከምንተዋብ መኝታ ቤት ከተሰደደ ሰነባብቷል፡፡
ከመኝታዋ ተነሳች፡፡ ከመኝታ ክፍሏ በመውጠት ከጐኗ ያለውን የልጇን መኝታ ክፍል ተመለከተች እና ስለእሱ አሰበች
‹‹ልጄ ንብረትህን ለበላተኛ አስረከብኩብህ ፡፡ ባክህ ማረኝ፡፡በድዬሀለው ይቅር በለኝ››ስትል ብቸዋን አጉተመተመች፡፡እንባዋን በዓይኖቾ ግጥም አለባት፡፡ከተገተረችበት ተንቀሳቀሰችና እርምጃዋን ቀጠለች፡፡የመስታወት መኝታ ክፍል ገርበብ ብሎል፡፡ በተከፈተው በር አንገቷን አስግጋ ተመለከችና ለደቂቃዎች በገረሜታ አስተዋለቻት..፡፡በሚገርምና በተረጋጋ ሁኔታ ተዘረጋግታ ጭልጥ ባለ ዕንቅልፈ ውስጥ ተውጣለች
‹‹የታደልሽ …ምነው ፈጣሪ ለእኔም ለአንድ ለሊት እንኳን እፎይታ ሰጥተኝ የሰላም እቅልፍ መተኛት በቻልኩ››በማለት ተመኘች፡፡
ለካ አንድ ነገር ሲያጡት ነው ምን ያህል ጠቃሚ እንደሆነ መረዳት የሚችሉት..፡፡በሰላም ተኝቶ..አሪፍ ህልም አልሞ…ታድሶ መነሳት ቀላል እና ተራ ነገር ቢመስልም በዋጋ ሊተመን የማይችል ትልቅ ፀጋ ነው ፡፡ክፋቱ ግን እንዲህ አይነት የሰላም እንቅልፍ እና ጥሩ ህልም በብዙ ሺ ብር የማይገዛ ለሰላማዊ ህይወት የምግብን ያህል አስፈላጊ ነገር መሆኑን ለመረዳት እንዲህ እንደምትዋብ አጥተውት ካዩት ቡኃላ ነው የምር የሚገባው፡፡
ፊቷን አዙራ ወደ ሳሎን በረንዳ ወጣች፡፡ጨላማው ደማቅ ቢሆንም ጨረቃዋ ግን ሙሉ ነበረች፡፡ሙሉነቷ እንደሰዓሊዎች አላስጐመዣትም ፤እንደከዋክብት ተመራማሪዎች አልሳባትም፤በአጠቃላይ ጥሩ ስሜት እንዲፈጠርባት አላደረጋትም ፤እንደውም በተቃራኒው ውስጧ እርብሽብሽ አለባት…መከፋቷ ጠንክሮ የውስጧ ብሶት ከገደቡ አልፎ መንጠባጠብ ጀመረባት..፡፡
‹‹ግን ምን ሀጥያት ሰርቼ ይሆን ..?››ይሄንን ጥያቄ እራሷን ብትጠይቅም መልሱን ግን ከውስጦ ማግኘት አልቻለችም ፡፡ባል ሲሞት ሌላ ባል ማግባት በእሷ አልተጀመረ፡፡እንደማንኛውም ባሎ የሞተባት ሴት የሟች ባሏን አርባ አስቆርባ ፤ሰማንያ ደግሳ አብልታ፤ የሙት አመቱን መታሰቢያ ካከበረች ቡኃላ ነው ለሀዘን ስትለብስ የከረመችውን ጥቁር ልብስ አውልቃ ለሌላ ፍቅር ለሌላ ግንኙነት ዓይኗን የከፈተችው..አጋጣሚ ሆኖ የተከፈተው አይኖ በቅርቧ ያለውን ወርቅ አለማውን ላይ አረፈላት፡፡ አፈቀረችው… አገባችው..፡፡ታዲያ እዚህ ሁሉ ውስጥ የእሷ ጥፋት፤ የእሷ ሀጥያት ምኑላይ ነው …?
በረንዳ ላይ ምን ያህል ጊዜ እንዳሳለፈች ትዝ አይላትም ብቻ ከሀሳቧ ያባነናት ከውስጥ የሰማችው የበራፍ መከፈት እና መዘጋት ድምጽ ነው፡፡
‹‹ማነው? ››በማለት ተንቀሳቀሳ የሳሎኑን በራፉ ከፈተችና ወደ ውስጥ ገባች..ምንም አይነት እንቅስቀቃሴ አይታያትም፡፡የራሷን ጆሮ ተጠራጠረች..‹‹‹እያበድኩ ይሆን እንዴ?››እራሷን ጠየቀች፡፡በዝግታ እርምጃ ወደ መስታወት መኝታ ክፍል አመራች፡፡ክፍሏ እንደቅድሙ ገርበብ እንዳለ ነው፡፡ወደውጥ አንገቷን አስግጋ ተመለከተች …ከእንደ ቅድሙ የተዘረጋጋ የመስታወት አካል ግን አልጋው ላይ አይታይም ..የተዘበራረቀ ብርድ ልብስና አንሶላ እለዩ ላይ የተከመረት ባዶ አልጋ ብቻ….
‹‹ድምጽ መስማቴ ቅዠት አልነበረም ማለት ነው..መቼስ ፊኛዋ አይቋጥር.. ወደሽንት ቤት ሄዳ ይሆናል›› ስትል አሰበች፡፡ወደበረንዳዋ ልትመለሰ ፊቷን ስታዞር አሁንም ጆሮዋ ውስጥ የሆነ በዚህ ሰዓት መሰማት የሌለበት ድምጽ ጥልቅ አለባት፡፡ የሰው ድምፅ..ንግግር የመሰለ ድምጽ..ትኩረቷን ወደእዛ ላከች..ድምጹ ከልጇ መኝተ ክፍል አካባቢ የሚበተን መስላት፡፡..በመገረም ወደእዛው አመራች፡፡በደንብ ተጠጋችና ጆሮዋን ግድግዳው ላይ ለጥፋ ማድመጥ ጀመረች፡፡የወንድ እና የሴት ንግግር ነው፡፡
‹‹ለምን አትሰሚኝም ጥያቄሽን ልቀበል አይቻለኝም››
የልጇ ድምጽ ነው፡፡‹‹ወይ ጉድ በዚህን ሰዓት የምን ጥያቄ ይሆን…?››ምንትዋብ በውስጧ አብሰለሰለች፡፡ ከውስጥ የሚሰማው ንግግር ቀጥሏል
‹‹አውቃለው ብዙ ጊዜ ነግረኸኛል››
‹‹እናስ?››
‹‹እናማ የምትለው አይገባኝም….የቤታችሁ ሰራተኛ ብሆንም አንተን ከማፍቀር እራሴን ማቀብ አልተቻለኝም››
‹‹መስታወት አሁን ተረጋጊና ወደክፍልሽ ተመለሺ…ባይሆን ነገ በቀኑ እንነጋገራበታለን››
‹‹እንደዚህ ብለህ እኮ መአት ቀን አታለኸኛል፡፡››
‹‹ወድጄ አይደለም እኮ ታውቂያለሽ በጣም የምወዳት ፍቅረኛ አለቺኝ ፡፡ፈጽሞ እሷን ማጣት ስለማልፈልግ ከሌላ ከማንኛውም ሰው ጋር በፍቅር መነካካት አልፈልግም››
‹‹ያነው ትክክለኛ ምክንያትህ ወይስ የቤት ሰረተኛ በመሆኔ ደበርኩህ?››
‹‹መስታወት እኔ እኮ አንቺን እንደ እህቴ እንጂ እንደቤት ሰራተኛ አይቼሽ አላውቅም፤ እዚህ ቤት እንደ እህት እና ወንድም አብረን ነው ያደግነው..ሰራተኛ መሆንሽን አንቺ ስትነግሪኝ ብቻ ነው ትዝ የሚለኝ ..››
‹‹ውሳኔህ ግን ፍትሀዊ አይደለም››
‹‹እንዴት… ?ፍትህና ፍቅርን ደግሞ ምን አገናኛቸው…በፍቅር ውስጥ ፍትህ ቦታ የለውም…አንቺ የጫማሽ ሶል ተሰንጥቆ ውሀ እያስገባ ለምትወጂው ሰው ግን ተበድረሽ ጃኬት ገዝተሸ ልትሰጪው ትቺያለሽ?...ፍቅረኛሽ በሆነ አሸባሪ እጅ ገብቶ እጁ ከሚቆረጥ አንቺ አንገትሽን ሰጥተሸ መሞትን ትመርጪያለሽ…..ወይም የምትወጂው ሰው በሽታ ተይዞ ሆስፒታል ቢገባ እና እሱን የምታሳክሚበት ገንዘብ ብታጪ ወይም ሌላ አማራጭ ባይኖርሽ ሸርሙጠሸም ሆነ ብር ከሚሰጥሽ ወንድ ጋር ተኝተሸ የእሱን ህክምና በመክፈል ልታሳክሚውና ልታድኚው ትችያለሽ..ታዲያ እነዚህ በምሳሌ ከጠቀስኩልሽ ክስተቶች መካከል የትኛው ነው ፍትሀዊ የሚባለው… ?አየሽ በፍቅር ውስጥ ፍትህ ታናሽ ነች…ለዚህ ነው በፍቅር እና ጦርነት ውስጥ ሁሉ ነገር ትክክል ነው የሚባለው… ስለዚህ እኔም በሮዝ ላይ ያለኝ አቋም በፍቅር የተቃኘ ስለሆነ ትክክል አይደለህም ልትይኝ አትቺይም›
‹‹ቢሆንም…ለማታፈቅርህ.. ለአንተ ቅንጣት ደነታ ለሌላት ሴት ስትል የምታፈቅርህን ሴት መግፋት..ቢያንስ እሺ አታግባኝ ..ወይንም እንደፍቅረኛህ አትቁጠረኝ..ግን ቢያንስ በድብቅም ቢሆን ከፍቅርህ እንድቋደስና እቅፍህ ውስጥ እንድገባ ብትፈቅድልኝ ነፍሴ ትደሰት ነበር ..ማምሻም እኮ ዕድሜ ነው..››
‹‹አይ መስታወት ፍቅር ፍቅር ነው…አብሬሽ ምተኛው ሳቅርሽና ስታፈቅሪኝ ብቻ ነው››
‹‹ባክህ ዝም በል፤ይሄ ህግ እኔ ላይ ሲሆን ብቻ ነው የሚሰራው..ከማታፈቅርህ ጋር ትኖር የለ..››አንቧረቀችበት፡፡
ምንትዋብ ከዚህ በላይ መታገስ አልቻለችም..በራፍን በርግዳ ወደ ልጇ ክፍል ዘው ብላ ገባች፡፡መሀሪ ከተቀመጠበት የአልጋ ጠርዝ መስታወት ከተቀመጠችበት ወንበር ሁለቱም ተስፈንጥረው ተነሱና ቆሙ፡፡ ያልጠበቁት ስለሆነ ሁለቱም በእፍረት አንገታቸውን ወደምድር አቀረቀሩ ምንትዋብም ሁለቱንም እያፈራረቀች ለደቂቃ ያህል በፅሞና ከተመለከተቻቸው ቡኃላ
‹‹መኝታ ቤት መጋራት ከጀመራችሁ ቆየ እንዴ?››የአሽሙር ንግግሯን ተናገረች መልስ ሚሰጣት ስታጣ ቀጠለች
‹‹አንቺ ለካ ስራ ብዙ ነሽ ቀን በጉልበት ስራ ስትባክኚ ትውያለሽ ለሊት ደግሞ እዚ……አሁን ጨርሰሻል ወይስ እዚሁ ነው የምታድሪው?››መስታወት ምንም ሳትናገር ሹክክ ብላ ክፍሉን ለቃ ወደራሷ ክፍል አመራች፡፡መሀሪ ግን እንደተገተረ ነው ምንም እንኳን እራሱን የቻለ ለአቅመ
:
#ክፍል_ሶስት
:
✍ደራሲ-በዘረሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...አየሩ ቀዝቃዛ ሲሆን ለሊቱ ደግሞ ፀጥታ ያረበበበት ነው፡፡ምንትዋብ አልጋዋ ላይ ተዘርራ አይኖን ጣሪያ ላይ ሰክታ ታስባለች፡፡ምሽቱም ገፍቶ 7 ሰዓት ማለፉን ግድግዳው ላይ የተንጠጠለውን የወርቅ ቅብ የግድግዳ ሰዓት ይናገራል፡፡እንደ ድሮ ቢሆን ለምንትዋብ ይሄ ጥሩ የእንቅልፍ ሰዓት ነበር ፡፡አሁን ግን ታሪክ ተቀይሯል፡፡ እንቅልፍ ከምንተዋብ መኝታ ቤት ከተሰደደ ሰነባብቷል፡፡
ከመኝታዋ ተነሳች፡፡ ከመኝታ ክፍሏ በመውጠት ከጐኗ ያለውን የልጇን መኝታ ክፍል ተመለከተች እና ስለእሱ አሰበች
‹‹ልጄ ንብረትህን ለበላተኛ አስረከብኩብህ ፡፡ ባክህ ማረኝ፡፡በድዬሀለው ይቅር በለኝ››ስትል ብቸዋን አጉተመተመች፡፡እንባዋን በዓይኖቾ ግጥም አለባት፡፡ከተገተረችበት ተንቀሳቀሰችና እርምጃዋን ቀጠለች፡፡የመስታወት መኝታ ክፍል ገርበብ ብሎል፡፡ በተከፈተው በር አንገቷን አስግጋ ተመለከችና ለደቂቃዎች በገረሜታ አስተዋለቻት..፡፡በሚገርምና በተረጋጋ ሁኔታ ተዘረጋግታ ጭልጥ ባለ ዕንቅልፈ ውስጥ ተውጣለች
‹‹የታደልሽ …ምነው ፈጣሪ ለእኔም ለአንድ ለሊት እንኳን እፎይታ ሰጥተኝ የሰላም እቅልፍ መተኛት በቻልኩ››በማለት ተመኘች፡፡
ለካ አንድ ነገር ሲያጡት ነው ምን ያህል ጠቃሚ እንደሆነ መረዳት የሚችሉት..፡፡በሰላም ተኝቶ..አሪፍ ህልም አልሞ…ታድሶ መነሳት ቀላል እና ተራ ነገር ቢመስልም በዋጋ ሊተመን የማይችል ትልቅ ፀጋ ነው ፡፡ክፋቱ ግን እንዲህ አይነት የሰላም እንቅልፍ እና ጥሩ ህልም በብዙ ሺ ብር የማይገዛ ለሰላማዊ ህይወት የምግብን ያህል አስፈላጊ ነገር መሆኑን ለመረዳት እንዲህ እንደምትዋብ አጥተውት ካዩት ቡኃላ ነው የምር የሚገባው፡፡
ፊቷን አዙራ ወደ ሳሎን በረንዳ ወጣች፡፡ጨላማው ደማቅ ቢሆንም ጨረቃዋ ግን ሙሉ ነበረች፡፡ሙሉነቷ እንደሰዓሊዎች አላስጐመዣትም ፤እንደከዋክብት ተመራማሪዎች አልሳባትም፤በአጠቃላይ ጥሩ ስሜት እንዲፈጠርባት አላደረጋትም ፤እንደውም በተቃራኒው ውስጧ እርብሽብሽ አለባት…መከፋቷ ጠንክሮ የውስጧ ብሶት ከገደቡ አልፎ መንጠባጠብ ጀመረባት..፡፡
‹‹ግን ምን ሀጥያት ሰርቼ ይሆን ..?››ይሄንን ጥያቄ እራሷን ብትጠይቅም መልሱን ግን ከውስጦ ማግኘት አልቻለችም ፡፡ባል ሲሞት ሌላ ባል ማግባት በእሷ አልተጀመረ፡፡እንደማንኛውም ባሎ የሞተባት ሴት የሟች ባሏን አርባ አስቆርባ ፤ሰማንያ ደግሳ አብልታ፤ የሙት አመቱን መታሰቢያ ካከበረች ቡኃላ ነው ለሀዘን ስትለብስ የከረመችውን ጥቁር ልብስ አውልቃ ለሌላ ፍቅር ለሌላ ግንኙነት ዓይኗን የከፈተችው..አጋጣሚ ሆኖ የተከፈተው አይኖ በቅርቧ ያለውን ወርቅ አለማውን ላይ አረፈላት፡፡ አፈቀረችው… አገባችው..፡፡ታዲያ እዚህ ሁሉ ውስጥ የእሷ ጥፋት፤ የእሷ ሀጥያት ምኑላይ ነው …?
በረንዳ ላይ ምን ያህል ጊዜ እንዳሳለፈች ትዝ አይላትም ብቻ ከሀሳቧ ያባነናት ከውስጥ የሰማችው የበራፍ መከፈት እና መዘጋት ድምጽ ነው፡፡
‹‹ማነው? ››በማለት ተንቀሳቀሳ የሳሎኑን በራፉ ከፈተችና ወደ ውስጥ ገባች..ምንም አይነት እንቅስቀቃሴ አይታያትም፡፡የራሷን ጆሮ ተጠራጠረች..‹‹‹እያበድኩ ይሆን እንዴ?››እራሷን ጠየቀች፡፡በዝግታ እርምጃ ወደ መስታወት መኝታ ክፍል አመራች፡፡ክፍሏ እንደቅድሙ ገርበብ እንዳለ ነው፡፡ወደውጥ አንገቷን አስግጋ ተመለከተች …ከእንደ ቅድሙ የተዘረጋጋ የመስታወት አካል ግን አልጋው ላይ አይታይም ..የተዘበራረቀ ብርድ ልብስና አንሶላ እለዩ ላይ የተከመረት ባዶ አልጋ ብቻ….
‹‹ድምጽ መስማቴ ቅዠት አልነበረም ማለት ነው..መቼስ ፊኛዋ አይቋጥር.. ወደሽንት ቤት ሄዳ ይሆናል›› ስትል አሰበች፡፡ወደበረንዳዋ ልትመለሰ ፊቷን ስታዞር አሁንም ጆሮዋ ውስጥ የሆነ በዚህ ሰዓት መሰማት የሌለበት ድምጽ ጥልቅ አለባት፡፡ የሰው ድምፅ..ንግግር የመሰለ ድምጽ..ትኩረቷን ወደእዛ ላከች..ድምጹ ከልጇ መኝተ ክፍል አካባቢ የሚበተን መስላት፡፡..በመገረም ወደእዛው አመራች፡፡በደንብ ተጠጋችና ጆሮዋን ግድግዳው ላይ ለጥፋ ማድመጥ ጀመረች፡፡የወንድ እና የሴት ንግግር ነው፡፡
‹‹ለምን አትሰሚኝም ጥያቄሽን ልቀበል አይቻለኝም››
የልጇ ድምጽ ነው፡፡‹‹ወይ ጉድ በዚህን ሰዓት የምን ጥያቄ ይሆን…?››ምንትዋብ በውስጧ አብሰለሰለች፡፡ ከውስጥ የሚሰማው ንግግር ቀጥሏል
‹‹አውቃለው ብዙ ጊዜ ነግረኸኛል››
‹‹እናስ?››
‹‹እናማ የምትለው አይገባኝም….የቤታችሁ ሰራተኛ ብሆንም አንተን ከማፍቀር እራሴን ማቀብ አልተቻለኝም››
‹‹መስታወት አሁን ተረጋጊና ወደክፍልሽ ተመለሺ…ባይሆን ነገ በቀኑ እንነጋገራበታለን››
‹‹እንደዚህ ብለህ እኮ መአት ቀን አታለኸኛል፡፡››
‹‹ወድጄ አይደለም እኮ ታውቂያለሽ በጣም የምወዳት ፍቅረኛ አለቺኝ ፡፡ፈጽሞ እሷን ማጣት ስለማልፈልግ ከሌላ ከማንኛውም ሰው ጋር በፍቅር መነካካት አልፈልግም››
‹‹ያነው ትክክለኛ ምክንያትህ ወይስ የቤት ሰረተኛ በመሆኔ ደበርኩህ?››
‹‹መስታወት እኔ እኮ አንቺን እንደ እህቴ እንጂ እንደቤት ሰራተኛ አይቼሽ አላውቅም፤ እዚህ ቤት እንደ እህት እና ወንድም አብረን ነው ያደግነው..ሰራተኛ መሆንሽን አንቺ ስትነግሪኝ ብቻ ነው ትዝ የሚለኝ ..››
‹‹ውሳኔህ ግን ፍትሀዊ አይደለም››
‹‹እንዴት… ?ፍትህና ፍቅርን ደግሞ ምን አገናኛቸው…በፍቅር ውስጥ ፍትህ ቦታ የለውም…አንቺ የጫማሽ ሶል ተሰንጥቆ ውሀ እያስገባ ለምትወጂው ሰው ግን ተበድረሽ ጃኬት ገዝተሸ ልትሰጪው ትቺያለሽ?...ፍቅረኛሽ በሆነ አሸባሪ እጅ ገብቶ እጁ ከሚቆረጥ አንቺ አንገትሽን ሰጥተሸ መሞትን ትመርጪያለሽ…..ወይም የምትወጂው ሰው በሽታ ተይዞ ሆስፒታል ቢገባ እና እሱን የምታሳክሚበት ገንዘብ ብታጪ ወይም ሌላ አማራጭ ባይኖርሽ ሸርሙጠሸም ሆነ ብር ከሚሰጥሽ ወንድ ጋር ተኝተሸ የእሱን ህክምና በመክፈል ልታሳክሚውና ልታድኚው ትችያለሽ..ታዲያ እነዚህ በምሳሌ ከጠቀስኩልሽ ክስተቶች መካከል የትኛው ነው ፍትሀዊ የሚባለው… ?አየሽ በፍቅር ውስጥ ፍትህ ታናሽ ነች…ለዚህ ነው በፍቅር እና ጦርነት ውስጥ ሁሉ ነገር ትክክል ነው የሚባለው… ስለዚህ እኔም በሮዝ ላይ ያለኝ አቋም በፍቅር የተቃኘ ስለሆነ ትክክል አይደለህም ልትይኝ አትቺይም›
‹‹ቢሆንም…ለማታፈቅርህ.. ለአንተ ቅንጣት ደነታ ለሌላት ሴት ስትል የምታፈቅርህን ሴት መግፋት..ቢያንስ እሺ አታግባኝ ..ወይንም እንደፍቅረኛህ አትቁጠረኝ..ግን ቢያንስ በድብቅም ቢሆን ከፍቅርህ እንድቋደስና እቅፍህ ውስጥ እንድገባ ብትፈቅድልኝ ነፍሴ ትደሰት ነበር ..ማምሻም እኮ ዕድሜ ነው..››
‹‹አይ መስታወት ፍቅር ፍቅር ነው…አብሬሽ ምተኛው ሳቅርሽና ስታፈቅሪኝ ብቻ ነው››
‹‹ባክህ ዝም በል፤ይሄ ህግ እኔ ላይ ሲሆን ብቻ ነው የሚሰራው..ከማታፈቅርህ ጋር ትኖር የለ..››አንቧረቀችበት፡፡
ምንትዋብ ከዚህ በላይ መታገስ አልቻለችም..በራፍን በርግዳ ወደ ልጇ ክፍል ዘው ብላ ገባች፡፡መሀሪ ከተቀመጠበት የአልጋ ጠርዝ መስታወት ከተቀመጠችበት ወንበር ሁለቱም ተስፈንጥረው ተነሱና ቆሙ፡፡ ያልጠበቁት ስለሆነ ሁለቱም በእፍረት አንገታቸውን ወደምድር አቀረቀሩ ምንትዋብም ሁለቱንም እያፈራረቀች ለደቂቃ ያህል በፅሞና ከተመለከተቻቸው ቡኃላ
‹‹መኝታ ቤት መጋራት ከጀመራችሁ ቆየ እንዴ?››የአሽሙር ንግግሯን ተናገረች መልስ ሚሰጣት ስታጣ ቀጠለች
‹‹አንቺ ለካ ስራ ብዙ ነሽ ቀን በጉልበት ስራ ስትባክኚ ትውያለሽ ለሊት ደግሞ እዚ……አሁን ጨርሰሻል ወይስ እዚሁ ነው የምታድሪው?››መስታወት ምንም ሳትናገር ሹክክ ብላ ክፍሉን ለቃ ወደራሷ ክፍል አመራች፡፡መሀሪ ግን እንደተገተረ ነው ምንም እንኳን እራሱን የቻለ ለአቅመ
❤2👍2
አዳም ከደረሰ አመታተን ያስቆጠረ ቢሆንም በዚህ ጉዳይ እናቱን ብዙም አይደፋራትም፡፡ምንዋብም በቆመችበት በልጇ ላይ ብታፈጥበትም ምን መናገር እንደለባት ግራ ገባት…ደግሞ ልጇን አጥፍተሀል ብሎ ለመቆጣት ምን የሞራል ብቃት አላት ?
‹‹በል ድህና እደር ››ብላ ከክፍሉ ለመውጣት ፈቷን አዙር ስትንቀሳቀስ ሳሎን ያለው ስልክ ተንጫረረ..ፍጥነቷን ጨምራ ወደ እዛው አመራች..
ኩማንደር መሀሪም ግራ ተጋባና ሰዓቱን ተመለከተ 7፤45 ይላል ፡፡‹‹በዚህ ሰዓት ማነው የሚደውለው?ያ ዕብድ ደረሰ እንዳይሆን ብቻ..?መቼስ እሱ ከሆነ በእዚህ ሰዓት ጥንብዝ ብሎ ሰክሮ መሆን አለበት..››ተጨነቀ
‹‹በስካር መንፈስ ዘባርቆ ጭራሽ ነገሮችን እንዳያባብስ ሰጋት ቀስፎ ያዘው ..እናቱን ተከትሎ ወደሳሎን ተንቀሰቀሰ ፡፡
//////
እናቱ ስልኩን አንስታ ማናገር ጀምራች
‹‹ለመሆኑ ነፍስህ አለ?››
‹‹መኖር ከተባለ?››
‹‹እንዴት ምን አጋጠመህ...?ለመሆኑ የት ነው ያለኸው ....?ደግሞ ሰው ያስባል አትልም እንዴ?››ግትልትል ጥያቄዎችን በአንዴ ደረደረችለት፡፡
ቀለም ወርቅ በተረጋጋ እና ለስለስ ባለ ድምጸት ከዛኛው የስልክ ጫፍ የሚያወራው ይሰማዋል‹‹ቀስ በይ እንጂ..እዬዬም ሲዳላ ነው ሲባል አልሰማሽም..ያልሻቸውን ነገረች ሁሉ ለማድረግ እኮ ማድረግ የምችልበት ሁኔታ ላይ መሆን አለብኝ››
በምንትዋብ አዕምሮ ውስጥ ለወራት የዘለቀው ስጋት እውን መሆኚያው ደቂቃ መቅረብን ሰውነቷ ነገራት…
‹‹የሆንከውን ልትነግረኝ ትችላለህ?››አለችው ተስፋ በመቁረጥ ጫፍ ላይ ባለ ስሜት
‹‹ መደወሌ እኮ የሆንኩትን ልነግርሽ ነው….››የምንትዋብ ሰውነት ሲንቀጠቀጥን የስልኩን እጄታ መያዝ አቅቷት ስትቸገር ከዛ እልፎ ለመውደቅ ስትንገዳገድ ልጇ መሀሪ በቅርብ እርቀት ሆኖ እየተመለከተ ነው፡፡እንደጠረጠረው ሰልኩን የደወለው ጓዳኛው ደረሰ ሳይሆን ያልጠቀው ቀለመወርቅ መሆኑ አስገርሞታል … አስፈርቶታልም፡፡
‹‹እሺ ንገረኝ..እያዳመጥኩህ ነው››
‹‹በደንብ አድምጪኝ አሁን ያለውት ሱዳን ነው፡፡በድንገት ቆንጇ ስራ አለ ብለውኝ ደላሎች አጭበርብረውኝ የንግድ ዕቃ ጭኜ ወደ ደቡብ ሱዳን ጁባ ነበር ያመረውት..፡፡እንደተባለውም ይዤ የሄኩትን ዕቃ እጥፍ በሆነ ትርፍ መሸጥ ችዬ ነበር፤ ግን ምን ዋጋ አለው ብሩን በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ብድኖች ድንገት ወረሩንና ደብድበውና ቀጥቅጠው ዘረፍኝ ..አሁን ባዶዬን አስቀርተውኛል፡፡ኤፍ.ኤስ.አር መኪናችንንም አቃጠሏት፡፡ ባዶዬን ቀርቼያለው..ይሄውልሽ…››
/////
የስልኩ እጄታ ከእጆ ተንሸራቶ ወደ መሬት ተምዘገዘገ ፡፡እሷም በአንድ ወገን ዘንበል ብላ ልትገነደስ ስትል ሁኔውን በተጠንቀቅ ቆሞ ሲከታተል የነበረው ልጇ ፈጠን ብሎ ደረሰላተትና ደጋግፎ ወደመኝታ ክፍሏ ወሰዳት፡፡
በዚህ ሰዓት በዚህ ሁኔታ ላይ ሆኖ የወሬውን ዝርዝር ሊጠይቃት አልፈለገም፡፡ ያንን ማድረግ ይበልጥ እንድትጨነቅ እና እንዳትረጋጋ ማድረግ ነው ብሎ ስላሰበ ተወው፡ከእዛ ይልቅ እንቅልፍ እንዲወስዳት አመቻችቶ አስተኛትና ክፍሉን መለስ አድርጐላት ወደ መኝታ ክፍሉ ተመለሶ ትካዜ ውስጥ ገባ፡፡እስከአሁን በቤቱ ነግሶ ከነበረው ጭንቀት ይልቅ በቀጣቹ ቀኖች የሚከሰተው ሁኔታ ጨለማ እንደሚሆን ሲታሰበው በሰውነቱን ቅጽበታዊ ቅዝቃዜ ተሰራጨ….ልቡ ድረስ የተሰማው ኩምትርትር የሚያደርግ ቅዝቃዜ….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
‹‹በል ድህና እደር ››ብላ ከክፍሉ ለመውጣት ፈቷን አዙር ስትንቀሳቀስ ሳሎን ያለው ስልክ ተንጫረረ..ፍጥነቷን ጨምራ ወደ እዛው አመራች..
ኩማንደር መሀሪም ግራ ተጋባና ሰዓቱን ተመለከተ 7፤45 ይላል ፡፡‹‹በዚህ ሰዓት ማነው የሚደውለው?ያ ዕብድ ደረሰ እንዳይሆን ብቻ..?መቼስ እሱ ከሆነ በእዚህ ሰዓት ጥንብዝ ብሎ ሰክሮ መሆን አለበት..››ተጨነቀ
‹‹በስካር መንፈስ ዘባርቆ ጭራሽ ነገሮችን እንዳያባብስ ሰጋት ቀስፎ ያዘው ..እናቱን ተከትሎ ወደሳሎን ተንቀሰቀሰ ፡፡
//////
እናቱ ስልኩን አንስታ ማናገር ጀምራች
‹‹ለመሆኑ ነፍስህ አለ?››
‹‹መኖር ከተባለ?››
‹‹እንዴት ምን አጋጠመህ...?ለመሆኑ የት ነው ያለኸው ....?ደግሞ ሰው ያስባል አትልም እንዴ?››ግትልትል ጥያቄዎችን በአንዴ ደረደረችለት፡፡
ቀለም ወርቅ በተረጋጋ እና ለስለስ ባለ ድምጸት ከዛኛው የስልክ ጫፍ የሚያወራው ይሰማዋል‹‹ቀስ በይ እንጂ..እዬዬም ሲዳላ ነው ሲባል አልሰማሽም..ያልሻቸውን ነገረች ሁሉ ለማድረግ እኮ ማድረግ የምችልበት ሁኔታ ላይ መሆን አለብኝ››
በምንትዋብ አዕምሮ ውስጥ ለወራት የዘለቀው ስጋት እውን መሆኚያው ደቂቃ መቅረብን ሰውነቷ ነገራት…
‹‹የሆንከውን ልትነግረኝ ትችላለህ?››አለችው ተስፋ በመቁረጥ ጫፍ ላይ ባለ ስሜት
‹‹ መደወሌ እኮ የሆንኩትን ልነግርሽ ነው….››የምንትዋብ ሰውነት ሲንቀጠቀጥን የስልኩን እጄታ መያዝ አቅቷት ስትቸገር ከዛ እልፎ ለመውደቅ ስትንገዳገድ ልጇ መሀሪ በቅርብ እርቀት ሆኖ እየተመለከተ ነው፡፡እንደጠረጠረው ሰልኩን የደወለው ጓዳኛው ደረሰ ሳይሆን ያልጠቀው ቀለመወርቅ መሆኑ አስገርሞታል … አስፈርቶታልም፡፡
‹‹እሺ ንገረኝ..እያዳመጥኩህ ነው››
‹‹በደንብ አድምጪኝ አሁን ያለውት ሱዳን ነው፡፡በድንገት ቆንጇ ስራ አለ ብለውኝ ደላሎች አጭበርብረውኝ የንግድ ዕቃ ጭኜ ወደ ደቡብ ሱዳን ጁባ ነበር ያመረውት..፡፡እንደተባለውም ይዤ የሄኩትን ዕቃ እጥፍ በሆነ ትርፍ መሸጥ ችዬ ነበር፤ ግን ምን ዋጋ አለው ብሩን በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ብድኖች ድንገት ወረሩንና ደብድበውና ቀጥቅጠው ዘረፍኝ ..አሁን ባዶዬን አስቀርተውኛል፡፡ኤፍ.ኤስ.አር መኪናችንንም አቃጠሏት፡፡ ባዶዬን ቀርቼያለው..ይሄውልሽ…››
/////
የስልኩ እጄታ ከእጆ ተንሸራቶ ወደ መሬት ተምዘገዘገ ፡፡እሷም በአንድ ወገን ዘንበል ብላ ልትገነደስ ስትል ሁኔውን በተጠንቀቅ ቆሞ ሲከታተል የነበረው ልጇ ፈጠን ብሎ ደረሰላተትና ደጋግፎ ወደመኝታ ክፍሏ ወሰዳት፡፡
በዚህ ሰዓት በዚህ ሁኔታ ላይ ሆኖ የወሬውን ዝርዝር ሊጠይቃት አልፈለገም፡፡ ያንን ማድረግ ይበልጥ እንድትጨነቅ እና እንዳትረጋጋ ማድረግ ነው ብሎ ስላሰበ ተወው፡ከእዛ ይልቅ እንቅልፍ እንዲወስዳት አመቻችቶ አስተኛትና ክፍሉን መለስ አድርጐላት ወደ መኝታ ክፍሉ ተመለሶ ትካዜ ውስጥ ገባ፡፡እስከአሁን በቤቱ ነግሶ ከነበረው ጭንቀት ይልቅ በቀጣቹ ቀኖች የሚከሰተው ሁኔታ ጨለማ እንደሚሆን ሲታሰበው በሰውነቱን ቅጽበታዊ ቅዝቃዜ ተሰራጨ….ልቡ ድረስ የተሰማው ኩምትርትር የሚያደርግ ቅዝቃዜ….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
❤1👍1