#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ_ጉዞ
:
#ክፍል_አስራ_አንድ
:
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...18 ዓመት ወጣትና የ12 ክፍል ተማሪ ሆኜ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለኝን ማትሪክ ፈተና ዝግጅት ላይ እያለው አስቀያሚ ነገር ተከሰተ፡፡አስቀያሚ ስላችሁ የመጨረሻ አስቀያሚ ማለቴ ነው፡፡ትምህርት ቤት ክፍል ውስጥ ቁጭ ብዬ በማማር ላይ ሳለው በስልኬ መልዕክት መጣ ፡፡ሳየው ከአያቴ ነው፡፡ያልተለመደ ነገር ነው፡፡የሚያስተምረውን አስተማሪ ትኩረት እንዳልስብ እየተጠነቀኩ ከፈትኩና አነብኩት….ደብተሬን እንኳን አልሰበሰብኩም፡፡ ተስፈንጥሬ ከመቀመጫዬ ተነሳው ፡፡ የክፍሉ ተማሪ አይን ከአስተማሪው ተነቅሎ ወደእኔ አነጣጠረ..አስተማሪው ማስተማሩን አቋርጦ ምን እንደሆንኩ መጠቅ ጀመረ …እየተንደረደርኩ ክፍሉን ለቅቄ ወጣው፡፡ሳይክል ሚጠቀሙ ተማሪዎች ሳይክላቸውን ወደሚያቆሙበት ስፋራ ነው የሮጥኩት፡፡ከመካከሉ ቁልፉ ያልተቆለፈውን አዋጣውና እየጋለብኩ ግቢወን ለቅቄ ወጣው፡፡ ሳይክሉ የማን እንደሆነ አላውቅም ግድም አልነበረኝም..
ሆስፒታል እንደደረስኩ ሳይኩል ወረድኩና ከመንገድ ዳር አጋድሜ ወደውስጥ ሮጥኩ… ኮሪደር ለኮሪደር እየተሸከረከርኩ አያቴን ወይንም ሌላ የማውቀው ሰው መፈለግ ጀመርኩ...አዎ አያቴን አገኘውት
-እናቴ የታለች …?እናቴ ምን ሆነች…??እማ!!
ተረጋጋ…ምን እንደሆነች አናውቅም…ድንገት ነው እራሷን የሳተችው ፡፡እያከሟት ነው፡፡ይውጡና ሚሉትን እንሰማለን፡፡››አለኝ አያቴ በሚርበተበት ድምፅ..
‹‹እራሴን መቆጣጠር አቃተኝ፡፡‹‹ቆይ አያቴ እንደዚህ አይነት ነገር እንዴት ይፈጠራል …?እናቴ ፍጽም ጤነኛ ነበረች፡፡እንኳን እራስ መሳት ይቅርና እራሷንም ሲያማት አይቼ አላውቅም ፡፡››
‹‹ለእኔም አንቆቅልሽ ነው የሆነብኝ ልጄ››አየቴ መለሰልኝ
ንግግሬን ሳልጨርስ እናቴ ስትታከምበት ከነበረው ክፍል አንድ ዶክተር ወጣ… ተንደርድረን ከበብነው፡፡ዶክተሩ እኔንና አያቴን ወደቢሮ ይዞን ሄደ፡፡ ካዘነው በላይ የሚያሳዝን …ከደነገጥነው በላይ የሚያስደነግጥ መርዶ ነገረን፡፡
‹‹የሚቀጥሉትን ሶስት ቀን እዚህ ትቆይና …ከዛ ትወስዶታላችሁ››
‹‹ተመስገን›› አለ አያቴ …ረጅም ግን ደግሞ ደካማ ትንፋሽ ተንፍሶ፡፡
‹‹ዶ/ር በሶስት ቀን ይሻላታል ማለት ነው…?››ጠየቅኩት በመፍለቅለቅ ….ለማረጋገጥ፡፡
ዶክተሩ አንገቱን እንደመድፋት አለና የተወሰነ አየር ወደውስጡ ስቦ ጭንቀት በሚለቅ ድምጽ ‹‹አዝናለው ..ይሻላታል ብዬ ተስፋ ልሰጣችሁ ብችል ደስ ይለኝ ነበር…ግን እሷን የማዳኑ ጉዳይ ረፍዶብናል››
‹‹ማለት …?››
እቤት ወስዳችሁ ያላትን ቀሪ አንድ ወርም ሆነ ሁለት ወር በደስታ አሳልፋ …በሰላም እንድታርፍ ከማድረግ ውጭ ሌላ ምርጫ የላችሁም፡፡››አለ የመለማመጥ ቃና ባለው ድምፀት፡፡
ከመቀመጫዬ ተንሳፍፌ ተነሳውና የሸሚዝኑን የጋወኑን ኮሌታ አንድ ላይ ጨምድጄ ከተቀመጠበት አንጠልጥዬ አስነሳውትና በአየር ላይ አንሳፍኩት…ሰውዬው አይኑ ተጉረጠረጠ..እጆቹን እንድለቀው ማወራጨቱን ቀጠለ
አያቴም ከድንዛዜው እንደምንም ባኖ ይለምነኝ ጀመር
‹‹ልጄ ምን እየሰራህ ነው..…?ሰውዬውን ልቀቀው..…?ልጄ የሰው ሰው እንዳትገል፡፡››
‹‹እናቴን ታድናታለህ አታድናትም.…?››አርገፍግፌ መሬት አድርሼ ለቀቅኩት
ዶክተሩ ጉሮሮውን በእጆቹ እየዳበሰ ደጋግሞ ካሳለ ቡኃላ‹‹.አዝናለው አልችልም…ማንም ሊያድናት አይችልም….››ብሎ ስለበሽታዋ አይነትና ከባድነት የደረሰበትን ደረጃ በተቆራረጠ ቃላት ይዘረዝርልን ቀጠለ.
በእናቴ ስም እምላለው…ከሞተች አገድልሀለው..አንተን ብቻ ሳይሆን ጠቅላላ እዚህ ግቢ ውስጥ ያላችሁትን ሀኪሞች ጨርሳችሆለው …ሆስፒታሉንም አቃጥለዋለው፡፡አረ ከተማወናም ነው የማቃጥለው…››በማለት ቢሮውን ጥዬ ወጣውና እናቴ ወደተኛችበት ክፍል ተንደረደርኩ ፡፡በራፍ ላይ የቆመችውን ነርስ ገፍቼ ፍቃዷንም ሳልጠይቅ ወደውስጥ ገባው፡፡እማዬ ዝርር ብላ ተሰትራ የሆስፒታሉ አልጋ ላይ ተኝታለች፡፡አይኖቾ ተከድነዋል፡፡ትንፋሿም አይሰማም ፡፡በሁለቱ አፍንጫጮ ቀዳዳ ቱቦ በክንዶቾ የግሉኮስ ላስቲክ ተሰክቶል፡፡
በራስጌዋ ሄድኩና ወለሉ ላይ ዝርፍጥ ብዬ ግንባሬን አልጋዋ ላይ ደፍቼ ወደ ፊቷ ተጠግቼ አስደገፍኩና በሹክሹክታ አወራት ጀመር….
ማሂ ምን እየሰራሽ ነው…?፡፡ምንድነው ዶክቱሩ የሚቀባጥረው…?፡፡ጥላህ ልትሄድ ነው እያለኝ ነው፡፡ስለማያውቅሽ ነው የሚቀባጥረው ፡፡አንቺ መቼም መቼም እኔን ጥለሽ መሄድ እንደማትችይ ስለማያውቅ ነው፡፡ገነትም ቢሆን እኔ ከሌለው መኖር እንደማትችይ ስለማውቅ ነው፡፡ማሂ ከተወለድኩበት ቀን አንስቶ ስትበይ እንብላ ብለሺኝ ስትተኚ እንተኛ ብለሺኝ ፤ስትተነፍሺ እንኳን የእኔንም መተንፈስ አረጋግጠሸ ነበር…ታዲያ ዶክተሮቹ እንደሚሊት አሁን ልትሞቺ ከሆነ እንዴት ልንሞት ነወ ተዘጋጅ ሳትይኝ .. …?ነገሩ ተይው እውነት ዶክተሩ አንዳለው ሸውደሺን ለመሞት የተዘጋጀሽ ከሆነም ግድ የለም እኔ ዝግጅት አያስፈልገኝም፡፡
ንግግሬን ከጀርባዬ ሆኖ ሲያዳምጥ የቆየው አያቴ በሽማግሌ አንጀቱ እየተንሰቀሰቀ በማልቀስ ዝቅ ብሎ አስነሳኝና
‹‹ተው ልጄ ተረጋጋ…አይዞህ እግዜር አለ ያድንልናል፡፡››
እንግዲህ እግዚያብሄር አለ የምትል ከሆነ በምትግባቡበት ቋንቋ ንገረው…ተው የሰው እናት አትንጠቅ በለው…እሷን አጥቶ መኖር አይችልም በለው…ከሰማህ ጥሩ ነው ፡፡ ካልሰማህ ደግሞ እኔንም ተሰናበተኝ ፡፡ እናም ከእናቴ ጋር በአንድ ጉድጓድ መቀበር ነው የምፈልገው..እንዳትረሳ በአንድ ጉድጓድ ፡፡ይህ ኑዛዜዬ ነው፡፡››ብዬው ጥዬው ወጣው ፡፡ወደየት እንደምሄድ ባላውቅም የሆስፒታሉን ቅጥር ጊቢ ለቅቄ ወጣው….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_አስራ_አንድ
:
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...18 ዓመት ወጣትና የ12 ክፍል ተማሪ ሆኜ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለኝን ማትሪክ ፈተና ዝግጅት ላይ እያለው አስቀያሚ ነገር ተከሰተ፡፡አስቀያሚ ስላችሁ የመጨረሻ አስቀያሚ ማለቴ ነው፡፡ትምህርት ቤት ክፍል ውስጥ ቁጭ ብዬ በማማር ላይ ሳለው በስልኬ መልዕክት መጣ ፡፡ሳየው ከአያቴ ነው፡፡ያልተለመደ ነገር ነው፡፡የሚያስተምረውን አስተማሪ ትኩረት እንዳልስብ እየተጠነቀኩ ከፈትኩና አነብኩት….ደብተሬን እንኳን አልሰበሰብኩም፡፡ ተስፈንጥሬ ከመቀመጫዬ ተነሳው ፡፡ የክፍሉ ተማሪ አይን ከአስተማሪው ተነቅሎ ወደእኔ አነጣጠረ..አስተማሪው ማስተማሩን አቋርጦ ምን እንደሆንኩ መጠቅ ጀመረ …እየተንደረደርኩ ክፍሉን ለቅቄ ወጣው፡፡ሳይክል ሚጠቀሙ ተማሪዎች ሳይክላቸውን ወደሚያቆሙበት ስፋራ ነው የሮጥኩት፡፡ከመካከሉ ቁልፉ ያልተቆለፈውን አዋጣውና እየጋለብኩ ግቢወን ለቅቄ ወጣው፡፡ ሳይክሉ የማን እንደሆነ አላውቅም ግድም አልነበረኝም..
ሆስፒታል እንደደረስኩ ሳይኩል ወረድኩና ከመንገድ ዳር አጋድሜ ወደውስጥ ሮጥኩ… ኮሪደር ለኮሪደር እየተሸከረከርኩ አያቴን ወይንም ሌላ የማውቀው ሰው መፈለግ ጀመርኩ...አዎ አያቴን አገኘውት
-እናቴ የታለች …?እናቴ ምን ሆነች…??እማ!!
ተረጋጋ…ምን እንደሆነች አናውቅም…ድንገት ነው እራሷን የሳተችው ፡፡እያከሟት ነው፡፡ይውጡና ሚሉትን እንሰማለን፡፡››አለኝ አያቴ በሚርበተበት ድምፅ..
‹‹እራሴን መቆጣጠር አቃተኝ፡፡‹‹ቆይ አያቴ እንደዚህ አይነት ነገር እንዴት ይፈጠራል …?እናቴ ፍጽም ጤነኛ ነበረች፡፡እንኳን እራስ መሳት ይቅርና እራሷንም ሲያማት አይቼ አላውቅም ፡፡››
‹‹ለእኔም አንቆቅልሽ ነው የሆነብኝ ልጄ››አየቴ መለሰልኝ
ንግግሬን ሳልጨርስ እናቴ ስትታከምበት ከነበረው ክፍል አንድ ዶክተር ወጣ… ተንደርድረን ከበብነው፡፡ዶክተሩ እኔንና አያቴን ወደቢሮ ይዞን ሄደ፡፡ ካዘነው በላይ የሚያሳዝን …ከደነገጥነው በላይ የሚያስደነግጥ መርዶ ነገረን፡፡
‹‹የሚቀጥሉትን ሶስት ቀን እዚህ ትቆይና …ከዛ ትወስዶታላችሁ››
‹‹ተመስገን›› አለ አያቴ …ረጅም ግን ደግሞ ደካማ ትንፋሽ ተንፍሶ፡፡
‹‹ዶ/ር በሶስት ቀን ይሻላታል ማለት ነው…?››ጠየቅኩት በመፍለቅለቅ ….ለማረጋገጥ፡፡
ዶክተሩ አንገቱን እንደመድፋት አለና የተወሰነ አየር ወደውስጡ ስቦ ጭንቀት በሚለቅ ድምጽ ‹‹አዝናለው ..ይሻላታል ብዬ ተስፋ ልሰጣችሁ ብችል ደስ ይለኝ ነበር…ግን እሷን የማዳኑ ጉዳይ ረፍዶብናል››
‹‹ማለት …?››
እቤት ወስዳችሁ ያላትን ቀሪ አንድ ወርም ሆነ ሁለት ወር በደስታ አሳልፋ …በሰላም እንድታርፍ ከማድረግ ውጭ ሌላ ምርጫ የላችሁም፡፡››አለ የመለማመጥ ቃና ባለው ድምፀት፡፡
ከመቀመጫዬ ተንሳፍፌ ተነሳውና የሸሚዝኑን የጋወኑን ኮሌታ አንድ ላይ ጨምድጄ ከተቀመጠበት አንጠልጥዬ አስነሳውትና በአየር ላይ አንሳፍኩት…ሰውዬው አይኑ ተጉረጠረጠ..እጆቹን እንድለቀው ማወራጨቱን ቀጠለ
አያቴም ከድንዛዜው እንደምንም ባኖ ይለምነኝ ጀመር
‹‹ልጄ ምን እየሰራህ ነው..…?ሰውዬውን ልቀቀው..…?ልጄ የሰው ሰው እንዳትገል፡፡››
‹‹እናቴን ታድናታለህ አታድናትም.…?››አርገፍግፌ መሬት አድርሼ ለቀቅኩት
ዶክተሩ ጉሮሮውን በእጆቹ እየዳበሰ ደጋግሞ ካሳለ ቡኃላ‹‹.አዝናለው አልችልም…ማንም ሊያድናት አይችልም….››ብሎ ስለበሽታዋ አይነትና ከባድነት የደረሰበትን ደረጃ በተቆራረጠ ቃላት ይዘረዝርልን ቀጠለ.
በእናቴ ስም እምላለው…ከሞተች አገድልሀለው..አንተን ብቻ ሳይሆን ጠቅላላ እዚህ ግቢ ውስጥ ያላችሁትን ሀኪሞች ጨርሳችሆለው …ሆስፒታሉንም አቃጥለዋለው፡፡አረ ከተማወናም ነው የማቃጥለው…››በማለት ቢሮውን ጥዬ ወጣውና እናቴ ወደተኛችበት ክፍል ተንደረደርኩ ፡፡በራፍ ላይ የቆመችውን ነርስ ገፍቼ ፍቃዷንም ሳልጠይቅ ወደውስጥ ገባው፡፡እማዬ ዝርር ብላ ተሰትራ የሆስፒታሉ አልጋ ላይ ተኝታለች፡፡አይኖቾ ተከድነዋል፡፡ትንፋሿም አይሰማም ፡፡በሁለቱ አፍንጫጮ ቀዳዳ ቱቦ በክንዶቾ የግሉኮስ ላስቲክ ተሰክቶል፡፡
በራስጌዋ ሄድኩና ወለሉ ላይ ዝርፍጥ ብዬ ግንባሬን አልጋዋ ላይ ደፍቼ ወደ ፊቷ ተጠግቼ አስደገፍኩና በሹክሹክታ አወራት ጀመር….
ማሂ ምን እየሰራሽ ነው…?፡፡ምንድነው ዶክቱሩ የሚቀባጥረው…?፡፡ጥላህ ልትሄድ ነው እያለኝ ነው፡፡ስለማያውቅሽ ነው የሚቀባጥረው ፡፡አንቺ መቼም መቼም እኔን ጥለሽ መሄድ እንደማትችይ ስለማያውቅ ነው፡፡ገነትም ቢሆን እኔ ከሌለው መኖር እንደማትችይ ስለማውቅ ነው፡፡ማሂ ከተወለድኩበት ቀን አንስቶ ስትበይ እንብላ ብለሺኝ ስትተኚ እንተኛ ብለሺኝ ፤ስትተነፍሺ እንኳን የእኔንም መተንፈስ አረጋግጠሸ ነበር…ታዲያ ዶክተሮቹ እንደሚሊት አሁን ልትሞቺ ከሆነ እንዴት ልንሞት ነወ ተዘጋጅ ሳትይኝ .. …?ነገሩ ተይው እውነት ዶክተሩ አንዳለው ሸውደሺን ለመሞት የተዘጋጀሽ ከሆነም ግድ የለም እኔ ዝግጅት አያስፈልገኝም፡፡
ንግግሬን ከጀርባዬ ሆኖ ሲያዳምጥ የቆየው አያቴ በሽማግሌ አንጀቱ እየተንሰቀሰቀ በማልቀስ ዝቅ ብሎ አስነሳኝና
‹‹ተው ልጄ ተረጋጋ…አይዞህ እግዜር አለ ያድንልናል፡፡››
እንግዲህ እግዚያብሄር አለ የምትል ከሆነ በምትግባቡበት ቋንቋ ንገረው…ተው የሰው እናት አትንጠቅ በለው…እሷን አጥቶ መኖር አይችልም በለው…ከሰማህ ጥሩ ነው ፡፡ ካልሰማህ ደግሞ እኔንም ተሰናበተኝ ፡፡ እናም ከእናቴ ጋር በአንድ ጉድጓድ መቀበር ነው የምፈልገው..እንዳትረሳ በአንድ ጉድጓድ ፡፡ይህ ኑዛዜዬ ነው፡፡››ብዬው ጥዬው ወጣው ፡፡ወደየት እንደምሄድ ባላውቅም የሆስፒታሉን ቅጥር ጊቢ ለቅቄ ወጣው….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍4❤2
#ስንቴ_ገረዝኩት✂️
:
#ክፍል_አንድ
:
:
✍ደራሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
“አንቺማ አትገርዢኝም። በስመአብ! ” አለ እያማተበ ለመቀመጥም ለመነሳትም በቀረበ አኳኋን አየሩ ላይ ተንጠልጥሎ።
“አየር ላይ ነህ፣ አረፍ ትል?” አልኩት አኳኋኑ ሳቄን እያመጣው
“የታለ ዶክተሩ ከምር? ” አለኝ ወንበሩ ላይ ተስተካክሎ እየተቀመጠ
“እኔ ነኝ!!” አልኩት ምን እንደሚያስብ ለመገመት እየሞከርኩ
ካርዱ ላይ የተፃፈው እድሜ 33 ይላል። ወጣት ነው፣ ማንም ሴት አይታው የምትደነግጥለት ዓይነት ቁመናና መልክ፤ በራሱ የሚተማመን የሚመስል ገፅታ ፤
“አንቺማ አትገርዢኝም። ይዤው አረጃታለሁ እንጂ………” አለኝ ለኔ ሳይሆን ለራሱ የሚያወራ በሚመስል ድምፅ
“ለምን? ሴት ስለሆንኩ?”
“አወና ፣ ሴት ብቻ አይደለሽም። ህልም የመሰልሽ ቆንጆ ሴት ነሽ። ሆ!!”
“እሱ ከስራዬ ጋር ምን አገናኘው?”
“ላንቺ ነዋ ስራ…………” ቀጥሎ ያልሰማሁትን ነገር አጉተመተመ
“ይቅርታ አቶ ሲሳይ ብዙ አገልግሎት ፈላጊዎች ውጪ ተሰልፈዋል። ስራችንን እንቀጥል?”
“እህ ስለተቆጣሽ ይሰማሽ መሰለሽ እንዴ?” አለ ወደሱሪው ዚፕ አይኑን እየላከ። መሳቅ አምሮኛል ግን መሳቅ የለብኝም።
“እንዴት ሳትገረዝ ……….?” ጥያቄዬን የምጨርስበት ቃል ስፈልግ
“አረጀህ? አይባልም ግን እሺ! ……….. ባክሽ አንጀት ነው ታሪኩ። ………… ተረት ነገር ነው የሚመስለው።”
“እየሰራሁ ታወራኛለሃ!!”
ብድግ ብሎ ገላውን አራቆተው።
“እንዴ እዚህ አይደለም የምሰራው።።።” አልኩት
“ቆይ ግን ትልቅ ወንድ ገርዘሽ ታውቂያለሽ?” አለኝ ምንም የተጋለጠ ሳይመስለው ተረጋግቶ ልብሱን ወደሰውነቱ እየመለሰ።
” አዎ። አውቃለሁ። ”
“እኔን የሚያህል?”
” ካንተም የሚበልጡ”
“ይሄን ነገር መቼም እንዲህ እንደቆመ አትገዘግዢውም አይደል?” እፍረት አይታይበትም። ስለቆመው አክሱም እንጂ ስለቆመው ንብረቱ ያወራ አይመስልም። በድጋሚ መሳቅ አምሮኛል። ፊቴን አዙሬ ፈገግታዬን ደበቅኩበት። ጭንቅላቴ ውስጥ ብቅ ያለው ሀሳብ ግን ቆሞ ነበር እንዴ? የሚለው ነበር። በየሱስ ስም!
“ማደንዘዣ እሰጥሃለሁ።”
“እህ! አይደለም ማደንዘዣ ፀሀይ የመሰልሽ ሴት ነክተሽው ሞቼ እንኳን ቢሆን አይቆምም?”
አሁን አለመሳቅ አልችልም ነበር። መጥሪያዬን ተጭኜ እጄን ከማንሳቴ ሲስተር ገባች።
“ኸረ ፍጥነት? በሩ ላይ ነበረች እንዴ? ” በማያገባው የሚገባ ሰው በቸልታ ማለፍ አልችልም እኮ ግን እንዳልሰማ ወደ ሲስተር ዞርኩ
”OR 2 ይዘጋጅልኝ። ማረፊያውን ታሳይሃለች እዛ ቆየኝ።” ካርዱን ለሲስተር አቀበልኳት። እሷ ያልኳትን ሰምታ ወጥታለች። እሱ እንደተቀመጠ በትዝብት ያየኛል።
“ምንድነው?”
“ይሄን ፊትሽን ግን ስሞትልሽ ፀብ ሲኖረኝ ሲኖረኝ እዋስሻለሁ። እንቢ እንዳትዪኝ! ኸረ በኪዳነምህረት!! “
“አቶ ሲሳይ የሚመለከተን ነገር ላይ ትኩረት እናድርግ?“
“you see እያናደድኩሽ እንኳን ፈገግ ብለሽ ነው የምትቆጪኝ። ምክንያቱም ደሞዝሽን የምከፍልሽ እኔ ነኛ! ባትመቺኝ ሌላ አማራጭ እንደምጠቀም ታውቂያለሽ። ስለዚህ ምን ያህል ስድ የሆነ costumer እንኳን ቢገጥምሽ በትህትና ታስተናግጃለሽ። ረዳቶችሽ ወደውሽ እንጂ ደመወዝ ስለምትከፍያቸው ፈርተውሽ እንዲታዘዙሽ አታድርጊ! እንደዛ ሲሆን አብረውሽ ያሉት ምርጫ እስካጡ ድረስ ብቻ ነው ማለት ነው።”
ልለው ያሰብኩት ብዙ ነበረ። ዋጋ ያለው ስላልመሰለኝ ተውኩትና እንዲወጣልኝ ብቻ በሩን አሳየሁት። ተነስቶ እየወጣ በሩን ተደግፎ ቆም አለና
«ያንቺን ስራ ደመወዝ ከፍለሽ እንደምታሰሪያቸው ሳይሆን እነርሱም የስራው አካል እንደሆኑ እንዲሰማቸው አድርጊ ያኔ ላንቺ ወይ ለደሞዝ ብለው ሳይሆን የራሳቸው ስራ መሆኑን ስለሚያስቡ ማንም ስራው እንዲበላሽበት አይፈልግም።»
«አቶ ሲሳይ ስድስት አመት ይሄን ሆስፒታል ቀጥ አድርጌ አስተዳርያለሁ። ሰራተኞቼን እንዴት መያዝ እንዳለብኝ አንተ አትነግረኝም!!» እንዴት ያለው ነው? እያናደደኝኮ ነው። ፈገግ ብሎ ከወጣ በኋላ መለስ ብሎ
«አይባልም ግን እሺ! ቤት ውስጥ የተቀጠረ ሰው እንኳን አሁን ቀርቷል ሰራተኛ አይባልም። ሆስተስ፣ አቀናባሪ ምናምን ነው የሚባለው። በሙያቸው የሚረዱሽን ሰዎች ሰራተኞቼ? ኸረ አይባልም!» ብሎኝ በሩን ዘጋው!! ኡፍፍፍፍፍፍፍፍ ምን አይነቱን ነው ዛሬ ደግሞ የጣለብኝ?
★ ★ ★
በሶስት ቀናት ውስጥ የተኛሁባቸው ሰዓታት 7 መሙላታቸውን እንጃ። እቤቴ ሄጄ አላውቅም። ተረኛ ታካሚ እስኪገባ ስጠብቅ እያወራ ወደ ውስጥ ዘለቀ።
“ስንቴ ነው የምትገርዢኝ?”
“ማለት?”
“ቁስሉ ተቦትርፎልሻል። ጨርሺኝ ብዬ ነው አንቺውጋ የመጣሁት።”
“አልገባኝም። እስኪ እዛጋ ሁንልኝ። ምን ሆኖ ነው?” አልኩት
“እኔ አንቺን ማሰብ ማቆም አቃተኝ። እሱም አለመቆም አቃተው። ተነፋፋሁ ሲል ቁስሉ ጣጣጣ…………” የሚያሾፍ ይመስላል። ቁስሉ ግን እንዳለው ቆስሎ ነበር።
“ስነስርዓት ባለው መንገድ እንደአዋቂዎች እናውራ?” አልኩት።ማንም ደንበኛ በዚህ መጠን ነፃነት እንዳወራኝ አላስታውስም።
“እኔ የምለው ማሂ?” አለ ኮስተር እንዳለ
” ዶክተር ማህደር” መለስኩለት
“ኡፍ! ከክብርና ከፍቅር የቱ ይበልጥ ይመስልሻል?”
“ሁለቱም ዋጋ ያላቸው የማይነፃፀሩ ነገሮች ናቸው።”
” ዶክተር ብልሽ ያከበርኩሽ ሊመስል ይችላል። ማሂ ስልሽ ግን ውዴታዬን እየነገርኩሽ ነው። ከክብር ሁሌም ፍቅር ይበልጣል። በክብር ውስጥ ፍቅር ላይኖር ይችላል። በፍቅር ውስጥ ግን ሁሌም ክብር አለ” የሆነ ነገሬን ያወቀ ስለመሰለኝ ተናደድኩ። ለተናገረው ትኩረት የሰጠሁ ባለመምሰል
“ጨርሻለሁ። ተጨማሪ አንድ መድሀኒት አዝልሃለሁ። በትክክል መድሀኒቱን ከወሰድክ በድጋሚ እዚህ መመላለስ አያስፈልግህም።” አልኩት
” OK አልጋ ልትሰጪኝ ማለት ነው? እሱ ጥሩ ሀሳብ ነው። ”
“አቶ ሲሳይ ለጨዋታ ጊዜ የለኝም።”
” ሊኖርሽ ግን ይገባል ማሂ!። ” መልስ ሳይጠብቅ የፃፍኩለትን ወረቀት ተቀብሎኝ ወጣ።
⚫️ይቀጥላል⚫️
ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳችሁ Like 👍 እያደረጋቹህ ምርጦቼ😘
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_አንድ
:
:
✍ደራሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
“አንቺማ አትገርዢኝም። በስመአብ! ” አለ እያማተበ ለመቀመጥም ለመነሳትም በቀረበ አኳኋን አየሩ ላይ ተንጠልጥሎ።
“አየር ላይ ነህ፣ አረፍ ትል?” አልኩት አኳኋኑ ሳቄን እያመጣው
“የታለ ዶክተሩ ከምር? ” አለኝ ወንበሩ ላይ ተስተካክሎ እየተቀመጠ
“እኔ ነኝ!!” አልኩት ምን እንደሚያስብ ለመገመት እየሞከርኩ
ካርዱ ላይ የተፃፈው እድሜ 33 ይላል። ወጣት ነው፣ ማንም ሴት አይታው የምትደነግጥለት ዓይነት ቁመናና መልክ፤ በራሱ የሚተማመን የሚመስል ገፅታ ፤
“አንቺማ አትገርዢኝም። ይዤው አረጃታለሁ እንጂ………” አለኝ ለኔ ሳይሆን ለራሱ የሚያወራ በሚመስል ድምፅ
“ለምን? ሴት ስለሆንኩ?”
“አወና ፣ ሴት ብቻ አይደለሽም። ህልም የመሰልሽ ቆንጆ ሴት ነሽ። ሆ!!”
“እሱ ከስራዬ ጋር ምን አገናኘው?”
“ላንቺ ነዋ ስራ…………” ቀጥሎ ያልሰማሁትን ነገር አጉተመተመ
“ይቅርታ አቶ ሲሳይ ብዙ አገልግሎት ፈላጊዎች ውጪ ተሰልፈዋል። ስራችንን እንቀጥል?”
“እህ ስለተቆጣሽ ይሰማሽ መሰለሽ እንዴ?” አለ ወደሱሪው ዚፕ አይኑን እየላከ። መሳቅ አምሮኛል ግን መሳቅ የለብኝም።
“እንዴት ሳትገረዝ ……….?” ጥያቄዬን የምጨርስበት ቃል ስፈልግ
“አረጀህ? አይባልም ግን እሺ! ……….. ባክሽ አንጀት ነው ታሪኩ። ………… ተረት ነገር ነው የሚመስለው።”
“እየሰራሁ ታወራኛለሃ!!”
ብድግ ብሎ ገላውን አራቆተው።
“እንዴ እዚህ አይደለም የምሰራው።።።” አልኩት
“ቆይ ግን ትልቅ ወንድ ገርዘሽ ታውቂያለሽ?” አለኝ ምንም የተጋለጠ ሳይመስለው ተረጋግቶ ልብሱን ወደሰውነቱ እየመለሰ።
” አዎ። አውቃለሁ። ”
“እኔን የሚያህል?”
” ካንተም የሚበልጡ”
“ይሄን ነገር መቼም እንዲህ እንደቆመ አትገዘግዢውም አይደል?” እፍረት አይታይበትም። ስለቆመው አክሱም እንጂ ስለቆመው ንብረቱ ያወራ አይመስልም። በድጋሚ መሳቅ አምሮኛል። ፊቴን አዙሬ ፈገግታዬን ደበቅኩበት። ጭንቅላቴ ውስጥ ብቅ ያለው ሀሳብ ግን ቆሞ ነበር እንዴ? የሚለው ነበር። በየሱስ ስም!
“ማደንዘዣ እሰጥሃለሁ።”
“እህ! አይደለም ማደንዘዣ ፀሀይ የመሰልሽ ሴት ነክተሽው ሞቼ እንኳን ቢሆን አይቆምም?”
አሁን አለመሳቅ አልችልም ነበር። መጥሪያዬን ተጭኜ እጄን ከማንሳቴ ሲስተር ገባች።
“ኸረ ፍጥነት? በሩ ላይ ነበረች እንዴ? ” በማያገባው የሚገባ ሰው በቸልታ ማለፍ አልችልም እኮ ግን እንዳልሰማ ወደ ሲስተር ዞርኩ
”OR 2 ይዘጋጅልኝ። ማረፊያውን ታሳይሃለች እዛ ቆየኝ።” ካርዱን ለሲስተር አቀበልኳት። እሷ ያልኳትን ሰምታ ወጥታለች። እሱ እንደተቀመጠ በትዝብት ያየኛል።
“ምንድነው?”
“ይሄን ፊትሽን ግን ስሞትልሽ ፀብ ሲኖረኝ ሲኖረኝ እዋስሻለሁ። እንቢ እንዳትዪኝ! ኸረ በኪዳነምህረት!! “
“አቶ ሲሳይ የሚመለከተን ነገር ላይ ትኩረት እናድርግ?“
“you see እያናደድኩሽ እንኳን ፈገግ ብለሽ ነው የምትቆጪኝ። ምክንያቱም ደሞዝሽን የምከፍልሽ እኔ ነኛ! ባትመቺኝ ሌላ አማራጭ እንደምጠቀም ታውቂያለሽ። ስለዚህ ምን ያህል ስድ የሆነ costumer እንኳን ቢገጥምሽ በትህትና ታስተናግጃለሽ። ረዳቶችሽ ወደውሽ እንጂ ደመወዝ ስለምትከፍያቸው ፈርተውሽ እንዲታዘዙሽ አታድርጊ! እንደዛ ሲሆን አብረውሽ ያሉት ምርጫ እስካጡ ድረስ ብቻ ነው ማለት ነው።”
ልለው ያሰብኩት ብዙ ነበረ። ዋጋ ያለው ስላልመሰለኝ ተውኩትና እንዲወጣልኝ ብቻ በሩን አሳየሁት። ተነስቶ እየወጣ በሩን ተደግፎ ቆም አለና
«ያንቺን ስራ ደመወዝ ከፍለሽ እንደምታሰሪያቸው ሳይሆን እነርሱም የስራው አካል እንደሆኑ እንዲሰማቸው አድርጊ ያኔ ላንቺ ወይ ለደሞዝ ብለው ሳይሆን የራሳቸው ስራ መሆኑን ስለሚያስቡ ማንም ስራው እንዲበላሽበት አይፈልግም።»
«አቶ ሲሳይ ስድስት አመት ይሄን ሆስፒታል ቀጥ አድርጌ አስተዳርያለሁ። ሰራተኞቼን እንዴት መያዝ እንዳለብኝ አንተ አትነግረኝም!!» እንዴት ያለው ነው? እያናደደኝኮ ነው። ፈገግ ብሎ ከወጣ በኋላ መለስ ብሎ
«አይባልም ግን እሺ! ቤት ውስጥ የተቀጠረ ሰው እንኳን አሁን ቀርቷል ሰራተኛ አይባልም። ሆስተስ፣ አቀናባሪ ምናምን ነው የሚባለው። በሙያቸው የሚረዱሽን ሰዎች ሰራተኞቼ? ኸረ አይባልም!» ብሎኝ በሩን ዘጋው!! ኡፍፍፍፍፍፍፍፍ ምን አይነቱን ነው ዛሬ ደግሞ የጣለብኝ?
★ ★ ★
በሶስት ቀናት ውስጥ የተኛሁባቸው ሰዓታት 7 መሙላታቸውን እንጃ። እቤቴ ሄጄ አላውቅም። ተረኛ ታካሚ እስኪገባ ስጠብቅ እያወራ ወደ ውስጥ ዘለቀ።
“ስንቴ ነው የምትገርዢኝ?”
“ማለት?”
“ቁስሉ ተቦትርፎልሻል። ጨርሺኝ ብዬ ነው አንቺውጋ የመጣሁት።”
“አልገባኝም። እስኪ እዛጋ ሁንልኝ። ምን ሆኖ ነው?” አልኩት
“እኔ አንቺን ማሰብ ማቆም አቃተኝ። እሱም አለመቆም አቃተው። ተነፋፋሁ ሲል ቁስሉ ጣጣጣ…………” የሚያሾፍ ይመስላል። ቁስሉ ግን እንዳለው ቆስሎ ነበር።
“ስነስርዓት ባለው መንገድ እንደአዋቂዎች እናውራ?” አልኩት።ማንም ደንበኛ በዚህ መጠን ነፃነት እንዳወራኝ አላስታውስም።
“እኔ የምለው ማሂ?” አለ ኮስተር እንዳለ
” ዶክተር ማህደር” መለስኩለት
“ኡፍ! ከክብርና ከፍቅር የቱ ይበልጥ ይመስልሻል?”
“ሁለቱም ዋጋ ያላቸው የማይነፃፀሩ ነገሮች ናቸው።”
” ዶክተር ብልሽ ያከበርኩሽ ሊመስል ይችላል። ማሂ ስልሽ ግን ውዴታዬን እየነገርኩሽ ነው። ከክብር ሁሌም ፍቅር ይበልጣል። በክብር ውስጥ ፍቅር ላይኖር ይችላል። በፍቅር ውስጥ ግን ሁሌም ክብር አለ” የሆነ ነገሬን ያወቀ ስለመሰለኝ ተናደድኩ። ለተናገረው ትኩረት የሰጠሁ ባለመምሰል
“ጨርሻለሁ። ተጨማሪ አንድ መድሀኒት አዝልሃለሁ። በትክክል መድሀኒቱን ከወሰድክ በድጋሚ እዚህ መመላለስ አያስፈልግህም።” አልኩት
” OK አልጋ ልትሰጪኝ ማለት ነው? እሱ ጥሩ ሀሳብ ነው። ”
“አቶ ሲሳይ ለጨዋታ ጊዜ የለኝም።”
” ሊኖርሽ ግን ይገባል ማሂ!። ” መልስ ሳይጠብቅ የፃፍኩለትን ወረቀት ተቀብሎኝ ወጣ።
⚫️ይቀጥላል⚫️
ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳችሁ Like 👍 እያደረጋቹህ ምርጦቼ😘
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍9❤1
#ስንቴ_ገረዝኩት ✂️
:
#ክፍል_ሁለት
:
:
✍ደረሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
....“ዶክተር? ያው ሰውዬ ነው የላከልሽ………” ሲስተር ቀለም በፈገግታ በደመቀ ፊት ጠረጴዛዬ ላይ በፎይል የተጠቀለለውን ምሳ አስቀምጣው ወደ በሩ ተመለሰች
“ሲስተር ከዛሬ በኋላ የሚያመጣውን ምሳ እንዳትቀበሉት።” አልኳት
ለሁለተኛ ጊዜ ታክሞ ከሄደ ጀምሮ ሶስት ቀኑ ነው። የምሳ ሰዓት እየጠበቀ ምሳ ይልካል። ጠዋት ፅዳቶቹ አፅድተው ሲጨርሱ አበባ ይልካል።
“አበባውንም ነው ዶክተር?”
“አዎን። ምንም ነገር!!”
“እሺ!!” ብላኝ ወጣች
ሲስተር ለምንድነው የምትሽቆጠቆጥልኝ? ስለምታከብረኝ? ደሞዝዋን ስለምከፍላት? አለቃዋ ስለሆንኩ? እንጂ አትወደኝም…………… ትጠላኝም ይሆናል። ይሄ የተረገመ ሰው ምን እንዳስብ እያደረገኝ ነው?
★ ★ ★
ሆዴ ምግብ አስፈልጎታል። ሆስፒታሉ አቅራቢያ ያለ ሬስቶራንት እራቴን ለመብላት አዝዤ ተቀምጫለሁ። ከየት መጣ ሳልል ከፊቴ ያለውን ወንበር ስቦ ተቀመጠ።
“ማሂ……ዬ……… ?” አለ በተሟዘዘ አጠራር
“አንተ ሰው ለምን አትተወኝም?”
“አቶ ሲሳይ ታፈሰ። ማዕረግ ያለኝ ሰው ነኝ እሺ።”
“Whatever አቶ ሲሳይ ምን እያሰብክ እንደሆነ አልገባኝም። እኔና አንተ ግን ምንም መሆን የምንችል ሰዎች አይደለንም።”
“ምክንያት? በእድሜ ስለምትበልጪኝ?”
“አቤት? ”
“በ18 ዓመትሽ ዩንቨርስቲ ብትገቢ፣ 7 ዓመት ዶክተር ለመባል ብትማሪ……”
“ዶክተር ለመሆን ” አቋረጥኩት
“ስፔሻሊስት ለመባል የሆነ ዓመት… …… ይሄን ሆስፒታል ከከፈትሽ 6 ዓመት… …… በስሱ 37 የግልሽ ነው። ”
እንዲያውቅብኝ ባልፈልግም ተናድጃለሁ። ለምን ተናደድኩ? ትክክለኛ እድሜዬን ስለነገረኝ። እና ምን አናደደኝ? ምክንያት እንኳን የለኝም።
“ቁስልህ ዳነልህ?” ወሬውን መቀየር ነው ፍላጎቴ
“እየደረቀ ነው። ላሳይሽ?” ከመቀመጫው ብድግ አለ
“ኸረ አንተ ሰው?” ለመቀመጥም ለመነሳትም በቀረበ አኳኋን አየሩ ላይ ተንሳፈፍኩ
“አየር ላይ ነሽ! አረፍ ትዪ……” ብሎኝ ተመልሶ ተቀመጠ
ያዘዝኩት ምግብ መጣ። ተነስቶ እጁን ታጥቦ እስኪመጣ ጠብቂኝ ባይለኝም ጠበቅኩት። የጠቀለለውን ሊያጎርሰኝ ዘረጋ
“ጉርሻ አልወድም።” አልኩት
“እንዴ? በሞቴ? በፍቅራችን?” ሆነ ብሎ ሬስቶራንት ውስጥ ያለው ሰው እንዲሰማ ጮክ ብሎ ነው የሚናገረው። ሰዎች እየዞሩ ያዩናል። ግማሾቹም ፈገግ እንደማለት ይላሉ። ጎረስኩለት።
“ማሂዬ ለክብርሽ ይሄን ያህል አትጨነቂ። ……” አለ የተናገረው ተራ ነገር እንደሆነ ሁሉ ለሌላ ጉርሻ እየተሰናዳ። ተበሳጭቻለሁ። ይበልጥ ያበሳጨኝ ደግሞ ያለው እውነት መሆኑ ነው።
“ክብር አንጃ ግራንጃህን ተወኝ። ባለትዳር ነኝ ለባለቤቴ …………”
ሳቁ አቋረጠኝ። አስቂኝ ተረት እንደነገሩት ህፃን ተንፈቀፈቀ::
“ምን ያስቅሃል?”
“ባለቤትሽ ነዋ ያሳቀኝ ሃሃሃሃ ”
“ምን ለማለት ፈልገህ ነው?”
” እንዳንቺ አይነት ሴቶች ወይ አላገቡም፣ ወይ አግብተው ፈተዋል፣ ወይ ከባላቸው ጋር ሰላም አይደሉም።”
“እኔ ምን ዓይነት ሴት ነኝ?”
“ካልኳቸው ምድብ ውስጥ ከሌለሽ ልቀጣ? እ?” መልሴን ጠበቀ
መልስ አልነበረኝም። ተነስቼ ጥዬው መሄድ ነበር ፍላጎቴ እግሮቼን ማዘዝ አቃተኝ። ሽንፈቴን መቀበልም መሰለኝ። ልከራከረውም አቅሙ አልነበረኝም።
“እኔ ምን አይነት ሴት ነኝ? ” ድምፄ የቅድሙ ጥንካሬ የለው
“እውቀትና ደረጃዋን ድክመትና ሽንፈቷን ለመሸፈን የምትጠቀም ዓይነት ሴት”
ከዚህ በላይ መስማት የሚያሳምመኝ መሰለኝ። ተነስቼ ስወጣ ድምፁ ተከትሎኛል።
“አየሽ አንቺ ይህቺ ነሽ። ትፈረጥጫለሽ።”
እኔ ምን አይነት ሴት ነኝ? የትኛውን ሽንፈቴን ነው በደረጃዬ የሸፈንኩት?
★ ★ ★
ወትሮም ለእንቅልፍ እምብዛም የሆነው ዓይኔ ጭራሽ አልከደን አለ። እቤቴን ጠላሁት። ልብሴን ለመቀየር ካልሆነ በቀር አዳሬም ሆስፒታል ከሆነ ሰነባበትኩ። ምግቤንም የምመገበው እዛው እያስመጣሁ ሆነ። ከዛ ቀን በኋላ ሲሳይን አላገኘሁትም። ከዛ ቀን በኋላ ግን ስላወራናቸው ነገሮች አለማሰብ አቃተኝ። ሁኔታዬን ይብስ ያባባሰው ደግሞ ከቀናት በፊት የገጠመኝ ነገር ነው። ዶክተር ሰይፈ!!! በግምት የ12 አመት ልጅ የምትሆን ህፃን በዊልቸር እየገፋ ሲያልፍ ነበር ያየሁት። ደሜ ሰውነቴ ውስጥ ሲቀዘቅዝ ታውቆኝ ነበር።
«ሲስተር? ዶክተር ሰይፈ ልጅ አለው እንዴ? » ቢሮ እንደገባሁ ጠየቅኳት። ጥያቄዬ ይሁን ሰይፈ የትኛው መሆኑ ግራ ያጋባት አልገባኝም። « ዶክተር ሰይፈ የህፃናት……………»
«እኮ ገብቶኛል። መጠየቅሽ ገርሞኝ ነው። አዎን ሁለት ሴት ልጆች አሉት። አንዷ ልጁ የመኪና አደጋ ደርሶባት she is totally paralyzed እሱ ነው የሚንከባከባት። አይኗም የማየት አቅሙ እየተዳከመ ነው።» አነጋገሯ ውስጥ ያለው ድምፀት ያሳምማል። አንቺ ምን ግድ አለሽ አይነት ነው።
« ሚስቱስ?»
«ህምምም……. ሚስቱ እኮ ሞታለች ዶክተር!»
« ለምን አልነገራችሁኝም? እንዴት አንድ ሰው አይነግረኝም?» ፀፀቴን ማራገፊያ አጥቼ እንጂ እሷ ላይ የምጮህበት ምክንያትም መብትም የለኝም።
« ምን ብለን? ዶክተር አንቺ ልብ ስለማትዪ እንጂ እኮ ለህክምና እዚህ ትመላለሳለች።» ብላኝ በመገረም እያየችኝ ወጣች።
ኡፍፍፍፍፍፍፍ በየሱስ ስም ምንድነው የሰራሁት? ዶክተር ሰይፈ በሙያው ማንም እንከን የማያወጣለት ጎበዝ ነው። በተደጋጋሚ እያረፈደ እና እየቀረ ስላስቸገረ ቦርዱን ሰብስቤ ከስራው እንዲባረር ያደረግኩት ቀን ያሳየኝን ፊት ትርጉም የምረዳው አሁን ነው። ምክንያቱን እንኳን ሊነግረኝ የደከመው ነበር የሚመስለው። እሺ ብቻ ነበር ያለኝ። ከቦርድ አባላቱ አንዱ ምክንያቱን እንድሰማው ጠይቆኝ ነበር። «ተውት ምክንያቴን ለእናንተ እያስረዳሁ ህመሜን አላበዛም። ለእስከዛሬው ቆይታችን አመሰግናለሁ!» ያለው በሰአቱ ምን ያለ መስሎኝ ነው ከምንም ያልቆጠርኩት? እንዴት ግን አንዳቸው እንኳን ልጁን እያስታመመ ነው አይሉኝም? ይሄን ያህል ድንጋይ ልብ ያለኝ ነው የምመስላቸው? ይጠሉኛል ማለት ነው አይደል?
ማሰብ ይደክማል እንዴ? ማሰብ ደከመኝ:: ስልኬ መልዕክት መቀበሉን ነገረኝ። ከፈትኩት። የማላውቀው ቁጥር ነው።
“ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ አይነኬ የህይወት ክፍል አለው። ያን ሽሽት የሆነ ነገር ውስጥ ይደበቃል። ሌት ተቀን ህሙማንን ማገልገልሽ ለብዙዎች ታታሪነትሽን ይነግራቸዋል። ስራሽ መደበቂያሽ መሆኑን ግን አሳምረሽ ታውቂዋለሽ።”
ከሱ ውጪ ማንም አይሆንም። ቁጥሩን ደወልኩበት። ይሄ ደግሞ ሊያሳብደኝ ነው እንዴ ሀሳቡ?
“ምንድነው ከኔ የምትፈልገው? ምንድነው ግን ችግርህ?”
“ደህና እግዜአብሄር ይመስገን!! ምሳ እንኳን አይመቸኝም። እራት ቢሆንልኝ እመርጣለሁ።” አለኝ ዘና ብሎ።
ምን ልለው ነበር የደወልኩት? ቁጣዬን ምላሴ ላይ ምን ያልከሰክሰዋል?
“እራት ልጋብዝሽ?” አለኝ ዝምታዬን ተከትሎ። ምን እንደምመልስለት ግራ ገባኝ።
“ማሂ ፕሊስ?……… እኔ ደስ ብቻ ነው የሚለኝ። ዶክተር ማህደር እራት ተጋበዘችልኝ ብዬ ቀላል ሴት የሆንሽ አይመስለኝም።” የማስበውን እኔ ከስቤ ሳልጨርሰው ከሱ አፍ እሰማዋለሁ።
“የባለፈው ሬስቶራንት 12 ሰዓት ላይ ላግኝሽ! ውብ ቀን ዋዩ!!” ብሎኝ እንቢም እሺም ሳልለው ስልኩን ዘጋው።
⚫️ይቀጥላል⚫️
ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳችሁ Like👍👍 እያደረጋችሁ የኔ ምርጦች😘
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_ሁለት
:
:
✍ደረሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
....“ዶክተር? ያው ሰውዬ ነው የላከልሽ………” ሲስተር ቀለም በፈገግታ በደመቀ ፊት ጠረጴዛዬ ላይ በፎይል የተጠቀለለውን ምሳ አስቀምጣው ወደ በሩ ተመለሰች
“ሲስተር ከዛሬ በኋላ የሚያመጣውን ምሳ እንዳትቀበሉት።” አልኳት
ለሁለተኛ ጊዜ ታክሞ ከሄደ ጀምሮ ሶስት ቀኑ ነው። የምሳ ሰዓት እየጠበቀ ምሳ ይልካል። ጠዋት ፅዳቶቹ አፅድተው ሲጨርሱ አበባ ይልካል።
“አበባውንም ነው ዶክተር?”
“አዎን። ምንም ነገር!!”
“እሺ!!” ብላኝ ወጣች
ሲስተር ለምንድነው የምትሽቆጠቆጥልኝ? ስለምታከብረኝ? ደሞዝዋን ስለምከፍላት? አለቃዋ ስለሆንኩ? እንጂ አትወደኝም…………… ትጠላኝም ይሆናል። ይሄ የተረገመ ሰው ምን እንዳስብ እያደረገኝ ነው?
★ ★ ★
ሆዴ ምግብ አስፈልጎታል። ሆስፒታሉ አቅራቢያ ያለ ሬስቶራንት እራቴን ለመብላት አዝዤ ተቀምጫለሁ። ከየት መጣ ሳልል ከፊቴ ያለውን ወንበር ስቦ ተቀመጠ።
“ማሂ……ዬ……… ?” አለ በተሟዘዘ አጠራር
“አንተ ሰው ለምን አትተወኝም?”
“አቶ ሲሳይ ታፈሰ። ማዕረግ ያለኝ ሰው ነኝ እሺ።”
“Whatever አቶ ሲሳይ ምን እያሰብክ እንደሆነ አልገባኝም። እኔና አንተ ግን ምንም መሆን የምንችል ሰዎች አይደለንም።”
“ምክንያት? በእድሜ ስለምትበልጪኝ?”
“አቤት? ”
“በ18 ዓመትሽ ዩንቨርስቲ ብትገቢ፣ 7 ዓመት ዶክተር ለመባል ብትማሪ……”
“ዶክተር ለመሆን ” አቋረጥኩት
“ስፔሻሊስት ለመባል የሆነ ዓመት… …… ይሄን ሆስፒታል ከከፈትሽ 6 ዓመት… …… በስሱ 37 የግልሽ ነው። ”
እንዲያውቅብኝ ባልፈልግም ተናድጃለሁ። ለምን ተናደድኩ? ትክክለኛ እድሜዬን ስለነገረኝ። እና ምን አናደደኝ? ምክንያት እንኳን የለኝም።
“ቁስልህ ዳነልህ?” ወሬውን መቀየር ነው ፍላጎቴ
“እየደረቀ ነው። ላሳይሽ?” ከመቀመጫው ብድግ አለ
“ኸረ አንተ ሰው?” ለመቀመጥም ለመነሳትም በቀረበ አኳኋን አየሩ ላይ ተንሳፈፍኩ
“አየር ላይ ነሽ! አረፍ ትዪ……” ብሎኝ ተመልሶ ተቀመጠ
ያዘዝኩት ምግብ መጣ። ተነስቶ እጁን ታጥቦ እስኪመጣ ጠብቂኝ ባይለኝም ጠበቅኩት። የጠቀለለውን ሊያጎርሰኝ ዘረጋ
“ጉርሻ አልወድም።” አልኩት
“እንዴ? በሞቴ? በፍቅራችን?” ሆነ ብሎ ሬስቶራንት ውስጥ ያለው ሰው እንዲሰማ ጮክ ብሎ ነው የሚናገረው። ሰዎች እየዞሩ ያዩናል። ግማሾቹም ፈገግ እንደማለት ይላሉ። ጎረስኩለት።
“ማሂዬ ለክብርሽ ይሄን ያህል አትጨነቂ። ……” አለ የተናገረው ተራ ነገር እንደሆነ ሁሉ ለሌላ ጉርሻ እየተሰናዳ። ተበሳጭቻለሁ። ይበልጥ ያበሳጨኝ ደግሞ ያለው እውነት መሆኑ ነው።
“ክብር አንጃ ግራንጃህን ተወኝ። ባለትዳር ነኝ ለባለቤቴ …………”
ሳቁ አቋረጠኝ። አስቂኝ ተረት እንደነገሩት ህፃን ተንፈቀፈቀ::
“ምን ያስቅሃል?”
“ባለቤትሽ ነዋ ያሳቀኝ ሃሃሃሃ ”
“ምን ለማለት ፈልገህ ነው?”
” እንዳንቺ አይነት ሴቶች ወይ አላገቡም፣ ወይ አግብተው ፈተዋል፣ ወይ ከባላቸው ጋር ሰላም አይደሉም።”
“እኔ ምን ዓይነት ሴት ነኝ?”
“ካልኳቸው ምድብ ውስጥ ከሌለሽ ልቀጣ? እ?” መልሴን ጠበቀ
መልስ አልነበረኝም። ተነስቼ ጥዬው መሄድ ነበር ፍላጎቴ እግሮቼን ማዘዝ አቃተኝ። ሽንፈቴን መቀበልም መሰለኝ። ልከራከረውም አቅሙ አልነበረኝም።
“እኔ ምን አይነት ሴት ነኝ? ” ድምፄ የቅድሙ ጥንካሬ የለው
“እውቀትና ደረጃዋን ድክመትና ሽንፈቷን ለመሸፈን የምትጠቀም ዓይነት ሴት”
ከዚህ በላይ መስማት የሚያሳምመኝ መሰለኝ። ተነስቼ ስወጣ ድምፁ ተከትሎኛል።
“አየሽ አንቺ ይህቺ ነሽ። ትፈረጥጫለሽ።”
እኔ ምን አይነት ሴት ነኝ? የትኛውን ሽንፈቴን ነው በደረጃዬ የሸፈንኩት?
★ ★ ★
ወትሮም ለእንቅልፍ እምብዛም የሆነው ዓይኔ ጭራሽ አልከደን አለ። እቤቴን ጠላሁት። ልብሴን ለመቀየር ካልሆነ በቀር አዳሬም ሆስፒታል ከሆነ ሰነባበትኩ። ምግቤንም የምመገበው እዛው እያስመጣሁ ሆነ። ከዛ ቀን በኋላ ሲሳይን አላገኘሁትም። ከዛ ቀን በኋላ ግን ስላወራናቸው ነገሮች አለማሰብ አቃተኝ። ሁኔታዬን ይብስ ያባባሰው ደግሞ ከቀናት በፊት የገጠመኝ ነገር ነው። ዶክተር ሰይፈ!!! በግምት የ12 አመት ልጅ የምትሆን ህፃን በዊልቸር እየገፋ ሲያልፍ ነበር ያየሁት። ደሜ ሰውነቴ ውስጥ ሲቀዘቅዝ ታውቆኝ ነበር።
«ሲስተር? ዶክተር ሰይፈ ልጅ አለው እንዴ? » ቢሮ እንደገባሁ ጠየቅኳት። ጥያቄዬ ይሁን ሰይፈ የትኛው መሆኑ ግራ ያጋባት አልገባኝም። « ዶክተር ሰይፈ የህፃናት……………»
«እኮ ገብቶኛል። መጠየቅሽ ገርሞኝ ነው። አዎን ሁለት ሴት ልጆች አሉት። አንዷ ልጁ የመኪና አደጋ ደርሶባት she is totally paralyzed እሱ ነው የሚንከባከባት። አይኗም የማየት አቅሙ እየተዳከመ ነው።» አነጋገሯ ውስጥ ያለው ድምፀት ያሳምማል። አንቺ ምን ግድ አለሽ አይነት ነው።
« ሚስቱስ?»
«ህምምም……. ሚስቱ እኮ ሞታለች ዶክተር!»
« ለምን አልነገራችሁኝም? እንዴት አንድ ሰው አይነግረኝም?» ፀፀቴን ማራገፊያ አጥቼ እንጂ እሷ ላይ የምጮህበት ምክንያትም መብትም የለኝም።
« ምን ብለን? ዶክተር አንቺ ልብ ስለማትዪ እንጂ እኮ ለህክምና እዚህ ትመላለሳለች።» ብላኝ በመገረም እያየችኝ ወጣች።
ኡፍፍፍፍፍፍፍ በየሱስ ስም ምንድነው የሰራሁት? ዶክተር ሰይፈ በሙያው ማንም እንከን የማያወጣለት ጎበዝ ነው። በተደጋጋሚ እያረፈደ እና እየቀረ ስላስቸገረ ቦርዱን ሰብስቤ ከስራው እንዲባረር ያደረግኩት ቀን ያሳየኝን ፊት ትርጉም የምረዳው አሁን ነው። ምክንያቱን እንኳን ሊነግረኝ የደከመው ነበር የሚመስለው። እሺ ብቻ ነበር ያለኝ። ከቦርድ አባላቱ አንዱ ምክንያቱን እንድሰማው ጠይቆኝ ነበር። «ተውት ምክንያቴን ለእናንተ እያስረዳሁ ህመሜን አላበዛም። ለእስከዛሬው ቆይታችን አመሰግናለሁ!» ያለው በሰአቱ ምን ያለ መስሎኝ ነው ከምንም ያልቆጠርኩት? እንዴት ግን አንዳቸው እንኳን ልጁን እያስታመመ ነው አይሉኝም? ይሄን ያህል ድንጋይ ልብ ያለኝ ነው የምመስላቸው? ይጠሉኛል ማለት ነው አይደል?
ማሰብ ይደክማል እንዴ? ማሰብ ደከመኝ:: ስልኬ መልዕክት መቀበሉን ነገረኝ። ከፈትኩት። የማላውቀው ቁጥር ነው።
“ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ አይነኬ የህይወት ክፍል አለው። ያን ሽሽት የሆነ ነገር ውስጥ ይደበቃል። ሌት ተቀን ህሙማንን ማገልገልሽ ለብዙዎች ታታሪነትሽን ይነግራቸዋል። ስራሽ መደበቂያሽ መሆኑን ግን አሳምረሽ ታውቂዋለሽ።”
ከሱ ውጪ ማንም አይሆንም። ቁጥሩን ደወልኩበት። ይሄ ደግሞ ሊያሳብደኝ ነው እንዴ ሀሳቡ?
“ምንድነው ከኔ የምትፈልገው? ምንድነው ግን ችግርህ?”
“ደህና እግዜአብሄር ይመስገን!! ምሳ እንኳን አይመቸኝም። እራት ቢሆንልኝ እመርጣለሁ።” አለኝ ዘና ብሎ።
ምን ልለው ነበር የደወልኩት? ቁጣዬን ምላሴ ላይ ምን ያልከሰክሰዋል?
“እራት ልጋብዝሽ?” አለኝ ዝምታዬን ተከትሎ። ምን እንደምመልስለት ግራ ገባኝ።
“ማሂ ፕሊስ?……… እኔ ደስ ብቻ ነው የሚለኝ። ዶክተር ማህደር እራት ተጋበዘችልኝ ብዬ ቀላል ሴት የሆንሽ አይመስለኝም።” የማስበውን እኔ ከስቤ ሳልጨርሰው ከሱ አፍ እሰማዋለሁ።
“የባለፈው ሬስቶራንት 12 ሰዓት ላይ ላግኝሽ! ውብ ቀን ዋዩ!!” ብሎኝ እንቢም እሺም ሳልለው ስልኩን ዘጋው።
⚫️ይቀጥላል⚫️
ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳችሁ Like👍👍 እያደረጋችሁ የኔ ምርጦች😘
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍12❤2
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ_
:
#ክፍል_አስራ_ሁለት
:
✍ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ሶስተኛ ቀን ነው፡፡እንደነጋ እናቴን ይዤ ከሆስፒታል ወደቤት እሄዳለው፡፡ከዛ አስክትሞትበት ቀን ድረስ አብሬያት ስሮ ተኛለው፡፡ስትነቃ ነቃለው ስትተኛ አብሬት ተኛለው፡፡ምንያህል እንድምወዳት ያለማቆረጥ በየቀኑ ነግራታለው፡፡የሚያስደስቷትን ዘፈኖች ዘፍንላታለው፡፡የሚያዝናናትን ታሪክ አወራታለው፡፡የሚትወዳቸውን ምግቦች ሁሉ በገዛ እጆቼ እያበሰልኩ እመግባታለው፡፡ከዛ የመጨረሻው ቀን ደርሶ ስትሞት ደቂቃዎችን ሳላባክን እከተላታለው፡፡እራሴን ለማጥፋት የሚያስፈልገኝ መሳረያ …. እንዴት እንደምሞት እቅድ አውጥጬ ዝግጅቴን ሁሉ ጨርሼያለው፡፡በዚህ ለሊት ሆስፒታል የበሽተኛ አልጋ ላይ ዝርግትግት ብላ ከተኛችወ እናቴ ጎን ካላ ሌላ አልጋ ላይ ተቀምጬ ነው እቅዴን እየከለስኩ ያለውት፡፡ሳላገባድድ የክፍሉ በረፍ በዝግታ ተከፈተ፡፡
በዚህ ሰዓት ነጭ ጋወን የለበሰ ባለሞያ እናቴ ወዳለችበት ክፍል ምምጣት የተለመደ ነገር ነው፡፡አዲስ የሆነው የመጣችው ልጅ ነች ፡፡በጥቁር እና በቅላት መካከል ያለ የሰውነት ከለር ፤የተመዘዘ የሰውነት ቁመት ያላት ቀጭን የምትባል ሀያዎቹ መጀመሪያ ላይ ያለች ፡፡በዚህ ለሊት ይሄ ሁሉ ፈግታ ገረመቺኝ፡፡ባለፉት ቀናት ልምዴ ሁሉም ዶክተሮች ሆኑ ነርሶች ለሊት ሲመጡ ከቀን ሁኔታቸው ባለይ ኮስተር ብለው ነው የማያቸው..ምን አልባ እንቅልፍ እየፈተናቸው ስለሚሆን ነው የሚል የራሴን ግምት ወስጄያለው..ምንም ቢሆን ሰው አይደሉ…?
ይህቺ ግን …ደግሞ ካለዛሬ ኮ አይቼያት አላውቅም፡፡
<<ተኝታለች…?››
<<አዎ ›
<<ወንድሞ ነህ…?››
ወንድሞም፤ጓደኛዋም፤ልጆም ነኝ››
‹‹ገባኝ …ግን እኩያዋ ነህ …ተናሽና ታላቅ እህትና ወንድም ነው የምትመስሉት፡፡በዚህ እድሜዋ አንተን ማድረሶ ሚገርም ነው፡፡››አለቺኝ በፈግታዋ እንደተሞላች በእጆ የያዘችውን እናቴን የህክምና የክትትል ሪከርድ እየተመለከተች
‹‹ልጆ መሆኔን አመንሽ ማለት ነው.…?አልኳት ..እንዴት እርግጠኛ ልትሆን እንደቻለች ግር ብሎኝ
‹‹አዎ ..አንዳንድ ነገሮችን ትንሽ ትኩረት ካደረግኩ ሳይነገረኝም ማወቅ እችላለው፡፡››
‹‹እሺ አንቼ በራፍን ከፍተሸ ከመምጣትሽ በፊት ምን እያሰብኩ ነበር››ዝም ብዬ ለቀልድ ያህል ነበር የጠየቅኳት…?
በእጆ የያዘችውን ወረቀት እናቴ የተኛችበት አልጋ ጠርዝ ላይ አስቀመጠችና በዝግታ እርምጃ ወደእኔ ተጠጋች .፡፡እንደመደንገጥ አልኩ‹‹እጅህን ስጠኝ ››አለቺኝ…ያለጥያቄ ቀኝ እጄን ዘረጋውላት፡፡ በሁለት እጆቾ መካከል አስገብታ ጨበጠችውና በመንፈስ ተሞልቶ እንደሚፀልይ ፓስተር አይኖቾን ጨፈነችና ለተወሰኑ ሰከንዶች ከቆየች ቡኃላ የመወርወር ያህል እጄን ለቃ ወደኃላ አፈገፈገችና ያስቀመጠችውን ወረቀት አንስታ ያዘች
‹‹ምነው ከበደሽ…?››
‹‹እናትህም ባንተ ቦታ ብትሆን እንደዛው ነበር የምታደርገው›› አለቺኝ
‹‹አልገባኝም››
‹‹የታመምከው እና ትሞታለህ የተባልከው አንተ ብትሆን እናትህም እንደአንተው እራሷን ለማጥፋት ዝግጅት ታደርግ ነበር..››
ከተቀመጥኩበት በድንጋጤ ተነሳውና ቆምኩ..መልሼ ቁጭ አልኩ
‹‹እንደዛ እያሰብኩ እንደሆነ እንዴት አወቅሽ…?››
‹‹እርሳው …አለቺኝና የእናቴን ሙቀት መለካት ጀመረች
‹‹አይ አረሳውም…ስለእናቴ የተጠቀሰው በሽታ የእውነት እንዳሉት በአጭር ቀናት ….››ዓ/ነገሩን ልጨርሰው አልቻልኩም፡፡
በብጫቂ ወረቀት ላይ ‹‹አዎ…እናትህ 25 ቀን ብቻ ነው ያላት፡፡››ብላ ፅፋ አቀበለቺኝ
እንደእኔ ሁሉ እሷም በአንደበቶ መናገር ከብዶት ይሁን ወይም እናቴ በእንቅልፍ ልቧም ቢሆን ልትሰማ ትችል ይሆናል ብላ በማሰብ አልገባኝም
ወረቀቱን ከነብኩ ቡኃለ ጠቅልዬ አፌ ውስጥ ከትኩት እና አኝኬ ዋጥኩት…ከዛ ፀጥ አልኩ…ምንም ልላት አልቻልኩም ፡፡የምታደርገውን አድርጋ በል አይዞህ በርታ ብላኝ እንደአመጣጦ ወጥታ ሄደች፡፡
መብሰልሰሌ በእጥፍ ጨመረ ..ይህቺ ዶክተር ማን ነች……?የእውነት ነች ወይስ ከመንፈስ ጋ እያወራው ነበርኩ…?››፡ከተቀመጥኩበት ተነሳውና ክፍሉን ለቅቄ ወጣው፡፡
ተረኛዋን ዶክተር ማናገር እንደምፈልግ ስናገር ቢሮዋ እንዳለች ጠቆሙኝ፡፡ሄድኩና በስሱ አንኳኳው፡፡
‹‹ግባ›› የሚል ድምፅ ከውስጥ ስሰማ …ከፈትኩና ገባው፡፡ አቀርቅራ መፅሀፍ እያነበበች ነበር፡፡አዎ የእውነት ነች ማለት ነው…? ፡፡እየቃዠው አይደለም፡፡
‹‹ቁጭ በል ››
ቁጭ አልኩ
‹‹ሳይሽ ዛሬ የመጀመሪያ ቀኔ ነው፡፡››
‹‹አዲስ ነኝ ፡፡ዛሬ ነው ስራ የጀመርኩት፡፡ይህቺ ለሊት የመጀመሪያ ቀኔ ነች፡፡››ብላ አስገረመቺኝ
‹‹ታዲያ እንዴት በመጀመሪያ ቀን ስራሽ እናቴን 28 ቀን እንደቀራት መናገር ቻልሽ…?››
አንደኛ የህክምና ውጤቱ ሪከርድ ተደርጓል፡፡እዚህ ፊት ለፊቴ ያለው ኮምፒተር ውስጥም አለ፡፡ወደእናንተ ከመምጣቴ በፊት አንብቤዋለው፡፡
‹‹28 ቀን ይቀራታል ይላል…?››ፍርጥም ብዬ ጠየቅኩ፡፡
‹‹አይ ቀኑንማ አይናገርም፡፡እሱ የእኔ ትንበያ ነው፡፡በነገራችን ላይ አንድ ውለታ ልውልልህ እያሰብኩ ነው፡፡››
‹‹ምን አይነት ውለታ…እናቴን የምትድነበት ሆስፒታል ወይም ሀገር ልትጠቁሚኝ ነው…?››
‹‹ፍጽም…እናትህን የሚያድናት ዘመናዊ ህክምና የትም ብትሄድ አታገኝም››
‹‹ታዲያ ሌላ ውለታ ምን ያደርግልኛል…?፡፡አልኮት ለምቦጬን ጥዬ
‹‹አንድ ማውቀው የባህል ህክምና አለ ፡፡ፈጽሞ አያድናትም ግን ቢያንስ ዕድሜዋን በሶስት አመት ያራዝመዋል፡፡››
ከተቀመጥኩበት በድንጋጤ ተነሳው.. ተንደርድሬ እግሯ ላይ ተደፋው…‹‹በፈጠረሽ ..በምታምኚው ይዤሻለው እባክሽ እናቴን አትሪፊልኝ››
‹‹ላተርፋት አልችልም…ሶስት አመት ብቻ›
‹‹ይሁን …ሶስት አመት .››
‹‹ሶስት አመት እኮ ብዙ አይደለም…ሳታስበው ነው የሚደርሰው››
ግድ የለሽም ..አንቺ ብቻ እሱን አድርጊልኝ… እስከዛ የሚሆነውን ማን ያውቃል…?፡፡››
‹‹እሺ ሂድ ከግማሽ ሰዓት ቡኃላ እመጣለው፡፡››
‹‹እመጣለው ስትይ..››
‹‹መድሀኒቱን ይዤ እመጣለው››
አላመንኳትም ፡፡እንዴ ባለፉት ሶስት ቀናቶች እንቅልፍ ባለመተኛቴ አዕምሮዬን እየሳትኩ ይሆን እንዴ …?ይሄ ነገር የእስካሁኑ ሁሉ ህልም እንዳይሆን..…?፡፡ጎንበስ አልኩና የእጄን መዳፍ ጠረጵዛዋ ላይ ዘረግቼ እጆ ላይ ያለውን እስኪሪብቶ ተቀበልኩና በኃይል ወጋውት .የእስኪሪብቶው ጫፍ የተወሰነ ጥልቀት ወደ መዳፌ ውስጥ ሲገባ እግሬ ድረስ ነዘረኝ..
‹‹በህልም ውስጥ አይደለውም ማለት ነው›…?አልኩ
‹‹ይሄ ያደረከው እኮ ማረጋገጫ አይሆንም ፡፡ምክንያቱም በህልምህም ቢሆን ይሄንን የማረጋገጫ ሙከራ ልትሞክር ትችላለህ ፡፡››ብላኝ ከስጋቴ እንዳልወጣ አደረገቺኝ…ለማንኛውም እንዳለቺኝ ቢሮዋን ለቅቄ ወደእናቴ ተመለስኩና በናፍቆትና በጭንቀት እጠብቃት ጀመር።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_አስራ_ሁለት
:
✍ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ሶስተኛ ቀን ነው፡፡እንደነጋ እናቴን ይዤ ከሆስፒታል ወደቤት እሄዳለው፡፡ከዛ አስክትሞትበት ቀን ድረስ አብሬያት ስሮ ተኛለው፡፡ስትነቃ ነቃለው ስትተኛ አብሬት ተኛለው፡፡ምንያህል እንድምወዳት ያለማቆረጥ በየቀኑ ነግራታለው፡፡የሚያስደስቷትን ዘፈኖች ዘፍንላታለው፡፡የሚያዝናናትን ታሪክ አወራታለው፡፡የሚትወዳቸውን ምግቦች ሁሉ በገዛ እጆቼ እያበሰልኩ እመግባታለው፡፡ከዛ የመጨረሻው ቀን ደርሶ ስትሞት ደቂቃዎችን ሳላባክን እከተላታለው፡፡እራሴን ለማጥፋት የሚያስፈልገኝ መሳረያ …. እንዴት እንደምሞት እቅድ አውጥጬ ዝግጅቴን ሁሉ ጨርሼያለው፡፡በዚህ ለሊት ሆስፒታል የበሽተኛ አልጋ ላይ ዝርግትግት ብላ ከተኛችወ እናቴ ጎን ካላ ሌላ አልጋ ላይ ተቀምጬ ነው እቅዴን እየከለስኩ ያለውት፡፡ሳላገባድድ የክፍሉ በረፍ በዝግታ ተከፈተ፡፡
በዚህ ሰዓት ነጭ ጋወን የለበሰ ባለሞያ እናቴ ወዳለችበት ክፍል ምምጣት የተለመደ ነገር ነው፡፡አዲስ የሆነው የመጣችው ልጅ ነች ፡፡በጥቁር እና በቅላት መካከል ያለ የሰውነት ከለር ፤የተመዘዘ የሰውነት ቁመት ያላት ቀጭን የምትባል ሀያዎቹ መጀመሪያ ላይ ያለች ፡፡በዚህ ለሊት ይሄ ሁሉ ፈግታ ገረመቺኝ፡፡ባለፉት ቀናት ልምዴ ሁሉም ዶክተሮች ሆኑ ነርሶች ለሊት ሲመጡ ከቀን ሁኔታቸው ባለይ ኮስተር ብለው ነው የማያቸው..ምን አልባ እንቅልፍ እየፈተናቸው ስለሚሆን ነው የሚል የራሴን ግምት ወስጄያለው..ምንም ቢሆን ሰው አይደሉ…?
ይህቺ ግን …ደግሞ ካለዛሬ ኮ አይቼያት አላውቅም፡፡
<<ተኝታለች…?››
<<አዎ ›
<<ወንድሞ ነህ…?››
ወንድሞም፤ጓደኛዋም፤ልጆም ነኝ››
‹‹ገባኝ …ግን እኩያዋ ነህ …ተናሽና ታላቅ እህትና ወንድም ነው የምትመስሉት፡፡በዚህ እድሜዋ አንተን ማድረሶ ሚገርም ነው፡፡››አለቺኝ በፈግታዋ እንደተሞላች በእጆ የያዘችውን እናቴን የህክምና የክትትል ሪከርድ እየተመለከተች
‹‹ልጆ መሆኔን አመንሽ ማለት ነው.…?አልኳት ..እንዴት እርግጠኛ ልትሆን እንደቻለች ግር ብሎኝ
‹‹አዎ ..አንዳንድ ነገሮችን ትንሽ ትኩረት ካደረግኩ ሳይነገረኝም ማወቅ እችላለው፡፡››
‹‹እሺ አንቼ በራፍን ከፍተሸ ከመምጣትሽ በፊት ምን እያሰብኩ ነበር››ዝም ብዬ ለቀልድ ያህል ነበር የጠየቅኳት…?
በእጆ የያዘችውን ወረቀት እናቴ የተኛችበት አልጋ ጠርዝ ላይ አስቀመጠችና በዝግታ እርምጃ ወደእኔ ተጠጋች .፡፡እንደመደንገጥ አልኩ‹‹እጅህን ስጠኝ ››አለቺኝ…ያለጥያቄ ቀኝ እጄን ዘረጋውላት፡፡ በሁለት እጆቾ መካከል አስገብታ ጨበጠችውና በመንፈስ ተሞልቶ እንደሚፀልይ ፓስተር አይኖቾን ጨፈነችና ለተወሰኑ ሰከንዶች ከቆየች ቡኃላ የመወርወር ያህል እጄን ለቃ ወደኃላ አፈገፈገችና ያስቀመጠችውን ወረቀት አንስታ ያዘች
‹‹ምነው ከበደሽ…?››
‹‹እናትህም ባንተ ቦታ ብትሆን እንደዛው ነበር የምታደርገው›› አለቺኝ
‹‹አልገባኝም››
‹‹የታመምከው እና ትሞታለህ የተባልከው አንተ ብትሆን እናትህም እንደአንተው እራሷን ለማጥፋት ዝግጅት ታደርግ ነበር..››
ከተቀመጥኩበት በድንጋጤ ተነሳውና ቆምኩ..መልሼ ቁጭ አልኩ
‹‹እንደዛ እያሰብኩ እንደሆነ እንዴት አወቅሽ…?››
‹‹እርሳው …አለቺኝና የእናቴን ሙቀት መለካት ጀመረች
‹‹አይ አረሳውም…ስለእናቴ የተጠቀሰው በሽታ የእውነት እንዳሉት በአጭር ቀናት ….››ዓ/ነገሩን ልጨርሰው አልቻልኩም፡፡
በብጫቂ ወረቀት ላይ ‹‹አዎ…እናትህ 25 ቀን ብቻ ነው ያላት፡፡››ብላ ፅፋ አቀበለቺኝ
እንደእኔ ሁሉ እሷም በአንደበቶ መናገር ከብዶት ይሁን ወይም እናቴ በእንቅልፍ ልቧም ቢሆን ልትሰማ ትችል ይሆናል ብላ በማሰብ አልገባኝም
ወረቀቱን ከነብኩ ቡኃለ ጠቅልዬ አፌ ውስጥ ከትኩት እና አኝኬ ዋጥኩት…ከዛ ፀጥ አልኩ…ምንም ልላት አልቻልኩም ፡፡የምታደርገውን አድርጋ በል አይዞህ በርታ ብላኝ እንደአመጣጦ ወጥታ ሄደች፡፡
መብሰልሰሌ በእጥፍ ጨመረ ..ይህቺ ዶክተር ማን ነች……?የእውነት ነች ወይስ ከመንፈስ ጋ እያወራው ነበርኩ…?››፡ከተቀመጥኩበት ተነሳውና ክፍሉን ለቅቄ ወጣው፡፡
ተረኛዋን ዶክተር ማናገር እንደምፈልግ ስናገር ቢሮዋ እንዳለች ጠቆሙኝ፡፡ሄድኩና በስሱ አንኳኳው፡፡
‹‹ግባ›› የሚል ድምፅ ከውስጥ ስሰማ …ከፈትኩና ገባው፡፡ አቀርቅራ መፅሀፍ እያነበበች ነበር፡፡አዎ የእውነት ነች ማለት ነው…? ፡፡እየቃዠው አይደለም፡፡
‹‹ቁጭ በል ››
ቁጭ አልኩ
‹‹ሳይሽ ዛሬ የመጀመሪያ ቀኔ ነው፡፡››
‹‹አዲስ ነኝ ፡፡ዛሬ ነው ስራ የጀመርኩት፡፡ይህቺ ለሊት የመጀመሪያ ቀኔ ነች፡፡››ብላ አስገረመቺኝ
‹‹ታዲያ እንዴት በመጀመሪያ ቀን ስራሽ እናቴን 28 ቀን እንደቀራት መናገር ቻልሽ…?››
አንደኛ የህክምና ውጤቱ ሪከርድ ተደርጓል፡፡እዚህ ፊት ለፊቴ ያለው ኮምፒተር ውስጥም አለ፡፡ወደእናንተ ከመምጣቴ በፊት አንብቤዋለው፡፡
‹‹28 ቀን ይቀራታል ይላል…?››ፍርጥም ብዬ ጠየቅኩ፡፡
‹‹አይ ቀኑንማ አይናገርም፡፡እሱ የእኔ ትንበያ ነው፡፡በነገራችን ላይ አንድ ውለታ ልውልልህ እያሰብኩ ነው፡፡››
‹‹ምን አይነት ውለታ…እናቴን የምትድነበት ሆስፒታል ወይም ሀገር ልትጠቁሚኝ ነው…?››
‹‹ፍጽም…እናትህን የሚያድናት ዘመናዊ ህክምና የትም ብትሄድ አታገኝም››
‹‹ታዲያ ሌላ ውለታ ምን ያደርግልኛል…?፡፡አልኮት ለምቦጬን ጥዬ
‹‹አንድ ማውቀው የባህል ህክምና አለ ፡፡ፈጽሞ አያድናትም ግን ቢያንስ ዕድሜዋን በሶስት አመት ያራዝመዋል፡፡››
ከተቀመጥኩበት በድንጋጤ ተነሳው.. ተንደርድሬ እግሯ ላይ ተደፋው…‹‹በፈጠረሽ ..በምታምኚው ይዤሻለው እባክሽ እናቴን አትሪፊልኝ››
‹‹ላተርፋት አልችልም…ሶስት አመት ብቻ›
‹‹ይሁን …ሶስት አመት .››
‹‹ሶስት አመት እኮ ብዙ አይደለም…ሳታስበው ነው የሚደርሰው››
ግድ የለሽም ..አንቺ ብቻ እሱን አድርጊልኝ… እስከዛ የሚሆነውን ማን ያውቃል…?፡፡››
‹‹እሺ ሂድ ከግማሽ ሰዓት ቡኃላ እመጣለው፡፡››
‹‹እመጣለው ስትይ..››
‹‹መድሀኒቱን ይዤ እመጣለው››
አላመንኳትም ፡፡እንዴ ባለፉት ሶስት ቀናቶች እንቅልፍ ባለመተኛቴ አዕምሮዬን እየሳትኩ ይሆን እንዴ …?ይሄ ነገር የእስካሁኑ ሁሉ ህልም እንዳይሆን..…?፡፡ጎንበስ አልኩና የእጄን መዳፍ ጠረጵዛዋ ላይ ዘረግቼ እጆ ላይ ያለውን እስኪሪብቶ ተቀበልኩና በኃይል ወጋውት .የእስኪሪብቶው ጫፍ የተወሰነ ጥልቀት ወደ መዳፌ ውስጥ ሲገባ እግሬ ድረስ ነዘረኝ..
‹‹በህልም ውስጥ አይደለውም ማለት ነው›…?አልኩ
‹‹ይሄ ያደረከው እኮ ማረጋገጫ አይሆንም ፡፡ምክንያቱም በህልምህም ቢሆን ይሄንን የማረጋገጫ ሙከራ ልትሞክር ትችላለህ ፡፡››ብላኝ ከስጋቴ እንዳልወጣ አደረገቺኝ…ለማንኛውም እንዳለቺኝ ቢሮዋን ለቅቄ ወደእናቴ ተመለስኩና በናፍቆትና በጭንቀት እጠብቃት ጀመር።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍11
#ስንቴ_ገረዝኩት ✂️
:
#ክፍል_ሶስት
:
:
✍ደረሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
....እግሬና ሀሳቤ ሳይስማሙ እግሬ ቀድሞ ሬስቶራንቱ ውስጥ ተገኘ። ሲሳይ ቀድሞኝ ተገኝቷል። ልጨብጠው የዘረጋሁትን እጄን ሳብ አድርጎ አቀፈኝ። የምቀመጥበትን ወንበር ሳበልኝ። እራትና ወይን አዘዝን። ከእርሱ ጋር መጨቃጨቁ ትርፉ የሌላ ሰው ትኩረት ከመሳብ ያለፈ ስለማይሆን ዝም ብዬ የሚያደርገውን ከማየት ውጪ ተቃውሞም መስማማትም አልተነፈስኩም። አፉ ከማውራት እጁ ከማጉረስ ሳይቦዝን ነበር እራት ተመግበን የጨረስነው።
“እኔ ከዚህ በላይ አልጠጣም። ስራ መመለስ አለብኝ።” ያልኩትን የሰማ አይመስልም። ቀዳልኝ። በአትኩሮት ሲመለከተኝ ከቆየ በኋላ
“ሴክስ ካደረግሽ ስንት ጊዜሽ ነው? ወራት? አመታት?” አለ ቀለል አድርጎ
“አንተ? ያምሃል እንዴ? ” አልኩት ደንግጬ ይሁን አፍሬ ሳይገባኝ
“ምነው? አንቺ? ጭራሽ… ……ዜሮ ዞሮ ነሽ እንዴ?” በማብሸቅ ለዛ ነው ያወራው ። ደሞ አብሽቆኛልም።
“አንተ እኔን ለማንጓጠጥ የሚያስችለህ ቦታ ላይ እንዳለህ ነው የሚሰማህ?” ሳልጨርስ መንፈቅፈቁን ያዘው
” ማሂ ከእኔ ጋር ስታወሪ ጨዋ ቃል አትፈልጊ…… ሃሃሃሃ ‘ትናንት እጄ ላይ ሸለፈትህን ተገርዘህ፣ ልጅህን በማስገረዣ እድሜህ አንዠርግገኸው…ምናምን ……‘ በይው ”
“እንደሱ ለማለት እንኳን አልነበረም።” መለስኩለት
“በጨዋኛ ስለብድ ምን ታውቅና? እንደማለት አይደል?”
“በየሱስ ስም!» ከመደንገጤ የተነሳ ወንበሬ ላይ ዘልያለሁ። እሱ ምንም እንዳላለ ሁሉ በሁኔታዬ ይንፈቀፈቃል።
“ያልተገረዘ ሴክስ አያደርግም ያለሽ ማነው?” አባባሉ ቀዝቃዛ ስሜት ስለነበረው ስሜቱን የጎዳሁት ስለመሰለኝ ወንዶች ስለማይገረዙባቸው ሀገራት፣ ገጥመውኝ ስለሚያውቁ አጋጣሚዎች ነገርኩት።
“ኮንዶም የለ፣ ምን የለ… … ጫፉን ሸብ አድርጎ መሰማራት ነው። ተፈጥሯዊ ኮንዶም በይው ሃሃሃ” ብልግና ያወራ፣ በራሱ ያላገጠ አይመስልም። ደንግጬ ፈጥጬ አየዋለሁ።
“ኸረ ስቀልድሽ ነው አንቺ!!” አለ መሳቁን ሳያቆም።
በህይወቱ ውስጥ የሚያስከፋው፣ የሚያፍርበት፣ ሊያወራው የማይፈልገው ነገሩ ምን ይሆን? ብዬ አሰብኩ። ሲያወራ ፍፁም ጨዋ፣ ደግሞ ፍፁም ባለጌ፣ ደግሞ ፍፁም አዋቂ፣ ደግሞ ፍፁም ህፃን………ሁሉንም ይሆናል። ሲሳይን ማወቅ ከበደኝ። ያልተገረዘው ቤተሰባቸው ወንድ ልጅ እየሞተ ሲያስቸግራቸው የሄዱበት ጠንቋይ እንዳይገረዝ ስለነገራቸው መሆኑን እንደለመደው በራሱና በቤተሰቡ እየቀለደ ነገረኝ።
“እያደግኩ ከመጣሁ በኋላ መገረዙ አሳፈረኝ እና አረጀሁ።”
“በፍፁም አፍረህበት የምታውቅ ግን አትመስልም ነበር።”
“አንቺጋ ስመጣማ ከማፈር አልፎ አስጠልቶኝ ነበር።”
ሲያወራ በራስ መተማመኑ ለሰከንድ አይለየውም። ደጋግሞ ከሚያወራቸው ነገሮች በወላጆቹና በ6 እህቶቹ የተለየ ፍቅር ተሰጥቶት እንደኖረ ገባኝ። ከብዙ ሰው ጋር መግባባቱ፣ ብዙ ጓደኞች ማፍራቱ ምናልባትም ከተማረው የሳይኮሎጂ ትምህርቱጋ ግንኙነት ይኖረው ይሆናል ስል አሰብኩ።
“ጓደኞች የሉሽም? የሆነ አብረሻቸው አንዳንዴ ዘና የምትዪበት ምናምን?”
“የሉኝም!!”
“እሺ ሲደብርሽ፣ ሲከፋሽ፣ ደስ ሲልሽ ወይ የተለየ ነገር ሲገጥምሽ ለማን ታወሪያለሽ?” አለኝ አይኖቹ የሚያነቡኝ ስለሚመስሉኝ እሸሻቸዋለሁ
“ለራሴ አወራዋለሁ።” አልኩት አይኑን ሳይሰብር አየኝ። “አንተስ?” አልኩት
“ያ ስሜት በተሰማኝ ሰዓት አጠገቤ ላገኘሁት ሰው። ለምሳሌ በኋላ ሸኝቼሽ ስመለስ ለሆስፒታላችሁ ዘበኛ ደስ እንዳለኝ ልነግረው እችላለሁ።” ቀለል አድርጎ ነው የሚያወራው
“እየቀለድክ ነው?”
“የምሬን ነው። ምነው?”
“የምልህ ከእኩዮችህ፣ ቢያንስ ከቤተሰብህ……… ባንተ ደረጃ ካሉ ሰዎች ጋር……… ” አላስጨረሰኝም።
“ደረጃ ምንድነው? ደረጃ መዳቢውስ ማነው? እኔን ከኒኛ ዘበኛ ወይ ከዚህ አስተናጋጅ በላይ ወይ በታች ደረጃ የሰጠን ማን ነው? የኔ መማር እና ቢሮ መቀመጥ? የሳቸው የእኔን እድል አለማግኘትና ዘበኛ መሆን? ንገሪኝ እስኪ እሳቸው የሚያውቁትን ወይ የሚችሉትን ደረጃ ብለን ባወጣንላቸው ዘበኝነት እንዴት እንመዝነዋለን?” አይቼበት የማላውቅበትን የለበጣ ፈገግታ ፈገግ ብሎ ቀጠለ
“አፈር ምን ደረጃ አለው? ነፍስስ ብትሆን ያው ነፍስ አይደለች? በምትሰራው ስራ ካልዳኘናት በቀር? የሰው ደረጃው ‘ሰውነቱ‘ ነው።” አለኝ። ዝም አልኩት። ምንስ ልለው እችል ነበር?
“ቤተሰቦችሽ? የት ናቸው?” አለኝ ወዲያው ከዛኛው ስሜት ወጥቶ
“ቤተሰቦቼ………?…… ”
“ምነው? ሞተዋል? ተጣልታችኋል? ወይስ…… እንደ እህል ዘርተውሽ ነው የበቀቀልሽው?…” ተናድጄ አቋረጥኩት ቁስሌን እያወራ እንደሆነ አልገባውም።
“ምንም ስነስርዓት አታውቅም። ባለጌ ነህ እሺ!!” አልኩት
“እሺ!” አለኝ ቁጣዬን ከምንም ሳይቆጥረው እጄን እየዳበሰ።
“እሺ ግን ንገሪኝ። ማወቅ እፈልጋለሁ።
ምኑን ልንገረው? አባቴ ከእህቱ ልጅ እንደወለደኝ እና ወንድ አያቴ እንዳሳደጉኝ? አድጌ ራሴን እስከማውቅ አባትና እናቴን እንደማላውቅ? ቤተሰቡ ውስጥ እንደ አንዳች መዓት ሲፀየፉኝ እንደኖርኩ? አያቴ ሲሞት ያየሁትን አስቀያሚ የህይወት ገፅታ? የቱን ልንገረው? ለማንም ለማውራት የሚቀል አልነበረም። እንባዬ መጣ። እያየኝ ማልቀስ አልፈለግኩም። ፈርጣጭ ይበለኝ። ተነስቼ መውጣት እንደጀመርኩ እንባዬን ማስቆም አቃተኝ።
ሬስቶራንቱን መግቢያ እንዳለፍኩ እሮጦ ደረሰብኝ። አቀፈኝ። እንደህፃን ደረቱ ላይ አጥብቆ አቀፈኝ። አለቀስኩ። አላባበለኝም። ፀጉሬን እየደባበሰና እየሳመ ለቅሶዬን እስክተው ጠበቀኝ። ያስለቀሰኝ ምን እንደነበረም አልጠየቀኝም። እንደተለመደው እያሳቀኝ የሆስፒታሉ መግቢያ ድረስ ሸኘኝ። ሲሰናበተኝ መልሶ አቀፈኝ። እቅፉ ውስጥ ብዙ መኖር ፈለግኩ። ከሆነ ነገር የሸሸገኝ መሰለኝ። ሰላም ያለበት ዓይነት። እሱም የገባው ይመስል አቅፎኝ ለደቂቃዎች ቆየ። ግንባሬን ሳመኝ።
“ዶክተር ሰላም አይደለሽም እንዴ?” ሲስተር ቀለም መግባቷንም አላስተዋልኩም።
“ሰላም ነው ሲስተር”
“ዶክተር ታዴ እየፈለገሽ ነው ኢመርጀንሲ ነው። ስልሽ እኮ አልሰማሽኝም።” እያወራችኝ የሻከረ መዳፏን ታፍተለትላለች።
እስከዛሬ እጇን አይቼው አላውቅም። ከድምፅዋ በቀር ምኗንም አስተውዬ አላውቅም። ለምንድ ነበር አውርቻት የማላውቀው? ለምንድነው ግንባሬን እንደቋጠርኩ ገብቼ የምወጣው? እንዲያከብሩኝ? ሲሳይ እንዳለኝ በራሴ ስለማልተማመን? ወይስ ደረጃዬን ስጠብቅ?
“ሲስተር ቤተሰብ አለሽ እንዴ?” አልኳት ለመሄድ እየተሰናዳሁ
“አዎን ባለትዳር ነኝ። አንድ ልጅም አለኝ። ምነው? ምን አጠፋሁ?”
ጉልበቴ ከዳኝ። ዞሬ አየኋት። በደቂቃ ብዙ ነገር አሰብኩ። ትፈራኛለች ምክኒያቱም ስራዋን ማጣት አትፈልግም። ከስራ ውጪ ስለምንም ነገር አውርቻት አላውቅም።ደሜ ቀዘቀዘ። እንዴት አይነት ጭራቅ አድርገው ነው የሚያስቡኝ?
“እንዲሁ ማወቅ ፈልጌ ነው።ለምን ትፈሪኛለሽ? አንቺ በጣም ታታሪ ሰራተኛ ነሽ እኮ!!” ትከሻዋን ዳበስ አድርጌ ወጣሁ።
★ ★ ★
ፈገግ እያልኩ መሆኔ ለራሴ ይታወቀኛል። ታካሚዎቼን እየፈገግኩ እንደማዋራቸው ገብቶኛል እያፏጨሁም መሰለኝ።ሰሞኑን በተደጋጋሚ ከሲሳይ ጋር እራቴን መብላቴን ተከትሎ እንደዚያ እየሆንኩ ነው ዶክተር ሰይፈን ይቅርታ መጠየቄ የሆነ ጭነት ከላዬ ላይ እንደማራገፍ ነበር ወደ ስራ እንዲመለስ የሚያስፈልገውን ሁሉ እንደማደርግ ስነግረው ግን
«ይቅርብኝ» ካለው ቃል በላይ ከቃሉ ጋር ከንፈሩን ነክሶ የፈገገው ፈገግታ ራሴን ደጋግሜ እንድረግም አድርጎኛል
ሲስተር ቀለም በተረኛ ታካሚ ፈንታ ገባች
“ዶክተር ሰው ይፈልግሻል?”
“ሲሳይ ነው? ትንሽ ታገሰኝ በይውና ተረኛ ታካሚ
:
#ክፍል_ሶስት
:
:
✍ደረሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
....እግሬና ሀሳቤ ሳይስማሙ እግሬ ቀድሞ ሬስቶራንቱ ውስጥ ተገኘ። ሲሳይ ቀድሞኝ ተገኝቷል። ልጨብጠው የዘረጋሁትን እጄን ሳብ አድርጎ አቀፈኝ። የምቀመጥበትን ወንበር ሳበልኝ። እራትና ወይን አዘዝን። ከእርሱ ጋር መጨቃጨቁ ትርፉ የሌላ ሰው ትኩረት ከመሳብ ያለፈ ስለማይሆን ዝም ብዬ የሚያደርገውን ከማየት ውጪ ተቃውሞም መስማማትም አልተነፈስኩም። አፉ ከማውራት እጁ ከማጉረስ ሳይቦዝን ነበር እራት ተመግበን የጨረስነው።
“እኔ ከዚህ በላይ አልጠጣም። ስራ መመለስ አለብኝ።” ያልኩትን የሰማ አይመስልም። ቀዳልኝ። በአትኩሮት ሲመለከተኝ ከቆየ በኋላ
“ሴክስ ካደረግሽ ስንት ጊዜሽ ነው? ወራት? አመታት?” አለ ቀለል አድርጎ
“አንተ? ያምሃል እንዴ? ” አልኩት ደንግጬ ይሁን አፍሬ ሳይገባኝ
“ምነው? አንቺ? ጭራሽ… ……ዜሮ ዞሮ ነሽ እንዴ?” በማብሸቅ ለዛ ነው ያወራው ። ደሞ አብሽቆኛልም።
“አንተ እኔን ለማንጓጠጥ የሚያስችለህ ቦታ ላይ እንዳለህ ነው የሚሰማህ?” ሳልጨርስ መንፈቅፈቁን ያዘው
” ማሂ ከእኔ ጋር ስታወሪ ጨዋ ቃል አትፈልጊ…… ሃሃሃሃ ‘ትናንት እጄ ላይ ሸለፈትህን ተገርዘህ፣ ልጅህን በማስገረዣ እድሜህ አንዠርግገኸው…ምናምን ……‘ በይው ”
“እንደሱ ለማለት እንኳን አልነበረም።” መለስኩለት
“በጨዋኛ ስለብድ ምን ታውቅና? እንደማለት አይደል?”
“በየሱስ ስም!» ከመደንገጤ የተነሳ ወንበሬ ላይ ዘልያለሁ። እሱ ምንም እንዳላለ ሁሉ በሁኔታዬ ይንፈቀፈቃል።
“ያልተገረዘ ሴክስ አያደርግም ያለሽ ማነው?” አባባሉ ቀዝቃዛ ስሜት ስለነበረው ስሜቱን የጎዳሁት ስለመሰለኝ ወንዶች ስለማይገረዙባቸው ሀገራት፣ ገጥመውኝ ስለሚያውቁ አጋጣሚዎች ነገርኩት።
“ኮንዶም የለ፣ ምን የለ… … ጫፉን ሸብ አድርጎ መሰማራት ነው። ተፈጥሯዊ ኮንዶም በይው ሃሃሃ” ብልግና ያወራ፣ በራሱ ያላገጠ አይመስልም። ደንግጬ ፈጥጬ አየዋለሁ።
“ኸረ ስቀልድሽ ነው አንቺ!!” አለ መሳቁን ሳያቆም።
በህይወቱ ውስጥ የሚያስከፋው፣ የሚያፍርበት፣ ሊያወራው የማይፈልገው ነገሩ ምን ይሆን? ብዬ አሰብኩ። ሲያወራ ፍፁም ጨዋ፣ ደግሞ ፍፁም ባለጌ፣ ደግሞ ፍፁም አዋቂ፣ ደግሞ ፍፁም ህፃን………ሁሉንም ይሆናል። ሲሳይን ማወቅ ከበደኝ። ያልተገረዘው ቤተሰባቸው ወንድ ልጅ እየሞተ ሲያስቸግራቸው የሄዱበት ጠንቋይ እንዳይገረዝ ስለነገራቸው መሆኑን እንደለመደው በራሱና በቤተሰቡ እየቀለደ ነገረኝ።
“እያደግኩ ከመጣሁ በኋላ መገረዙ አሳፈረኝ እና አረጀሁ።”
“በፍፁም አፍረህበት የምታውቅ ግን አትመስልም ነበር።”
“አንቺጋ ስመጣማ ከማፈር አልፎ አስጠልቶኝ ነበር።”
ሲያወራ በራስ መተማመኑ ለሰከንድ አይለየውም። ደጋግሞ ከሚያወራቸው ነገሮች በወላጆቹና በ6 እህቶቹ የተለየ ፍቅር ተሰጥቶት እንደኖረ ገባኝ። ከብዙ ሰው ጋር መግባባቱ፣ ብዙ ጓደኞች ማፍራቱ ምናልባትም ከተማረው የሳይኮሎጂ ትምህርቱጋ ግንኙነት ይኖረው ይሆናል ስል አሰብኩ።
“ጓደኞች የሉሽም? የሆነ አብረሻቸው አንዳንዴ ዘና የምትዪበት ምናምን?”
“የሉኝም!!”
“እሺ ሲደብርሽ፣ ሲከፋሽ፣ ደስ ሲልሽ ወይ የተለየ ነገር ሲገጥምሽ ለማን ታወሪያለሽ?” አለኝ አይኖቹ የሚያነቡኝ ስለሚመስሉኝ እሸሻቸዋለሁ
“ለራሴ አወራዋለሁ።” አልኩት አይኑን ሳይሰብር አየኝ። “አንተስ?” አልኩት
“ያ ስሜት በተሰማኝ ሰዓት አጠገቤ ላገኘሁት ሰው። ለምሳሌ በኋላ ሸኝቼሽ ስመለስ ለሆስፒታላችሁ ዘበኛ ደስ እንዳለኝ ልነግረው እችላለሁ።” ቀለል አድርጎ ነው የሚያወራው
“እየቀለድክ ነው?”
“የምሬን ነው። ምነው?”
“የምልህ ከእኩዮችህ፣ ቢያንስ ከቤተሰብህ……… ባንተ ደረጃ ካሉ ሰዎች ጋር……… ” አላስጨረሰኝም።
“ደረጃ ምንድነው? ደረጃ መዳቢውስ ማነው? እኔን ከኒኛ ዘበኛ ወይ ከዚህ አስተናጋጅ በላይ ወይ በታች ደረጃ የሰጠን ማን ነው? የኔ መማር እና ቢሮ መቀመጥ? የሳቸው የእኔን እድል አለማግኘትና ዘበኛ መሆን? ንገሪኝ እስኪ እሳቸው የሚያውቁትን ወይ የሚችሉትን ደረጃ ብለን ባወጣንላቸው ዘበኝነት እንዴት እንመዝነዋለን?” አይቼበት የማላውቅበትን የለበጣ ፈገግታ ፈገግ ብሎ ቀጠለ
“አፈር ምን ደረጃ አለው? ነፍስስ ብትሆን ያው ነፍስ አይደለች? በምትሰራው ስራ ካልዳኘናት በቀር? የሰው ደረጃው ‘ሰውነቱ‘ ነው።” አለኝ። ዝም አልኩት። ምንስ ልለው እችል ነበር?
“ቤተሰቦችሽ? የት ናቸው?” አለኝ ወዲያው ከዛኛው ስሜት ወጥቶ
“ቤተሰቦቼ………?…… ”
“ምነው? ሞተዋል? ተጣልታችኋል? ወይስ…… እንደ እህል ዘርተውሽ ነው የበቀቀልሽው?…” ተናድጄ አቋረጥኩት ቁስሌን እያወራ እንደሆነ አልገባውም።
“ምንም ስነስርዓት አታውቅም። ባለጌ ነህ እሺ!!” አልኩት
“እሺ!” አለኝ ቁጣዬን ከምንም ሳይቆጥረው እጄን እየዳበሰ።
“እሺ ግን ንገሪኝ። ማወቅ እፈልጋለሁ።
ምኑን ልንገረው? አባቴ ከእህቱ ልጅ እንደወለደኝ እና ወንድ አያቴ እንዳሳደጉኝ? አድጌ ራሴን እስከማውቅ አባትና እናቴን እንደማላውቅ? ቤተሰቡ ውስጥ እንደ አንዳች መዓት ሲፀየፉኝ እንደኖርኩ? አያቴ ሲሞት ያየሁትን አስቀያሚ የህይወት ገፅታ? የቱን ልንገረው? ለማንም ለማውራት የሚቀል አልነበረም። እንባዬ መጣ። እያየኝ ማልቀስ አልፈለግኩም። ፈርጣጭ ይበለኝ። ተነስቼ መውጣት እንደጀመርኩ እንባዬን ማስቆም አቃተኝ።
ሬስቶራንቱን መግቢያ እንዳለፍኩ እሮጦ ደረሰብኝ። አቀፈኝ። እንደህፃን ደረቱ ላይ አጥብቆ አቀፈኝ። አለቀስኩ። አላባበለኝም። ፀጉሬን እየደባበሰና እየሳመ ለቅሶዬን እስክተው ጠበቀኝ። ያስለቀሰኝ ምን እንደነበረም አልጠየቀኝም። እንደተለመደው እያሳቀኝ የሆስፒታሉ መግቢያ ድረስ ሸኘኝ። ሲሰናበተኝ መልሶ አቀፈኝ። እቅፉ ውስጥ ብዙ መኖር ፈለግኩ። ከሆነ ነገር የሸሸገኝ መሰለኝ። ሰላም ያለበት ዓይነት። እሱም የገባው ይመስል አቅፎኝ ለደቂቃዎች ቆየ። ግንባሬን ሳመኝ።
“ዶክተር ሰላም አይደለሽም እንዴ?” ሲስተር ቀለም መግባቷንም አላስተዋልኩም።
“ሰላም ነው ሲስተር”
“ዶክተር ታዴ እየፈለገሽ ነው ኢመርጀንሲ ነው። ስልሽ እኮ አልሰማሽኝም።” እያወራችኝ የሻከረ መዳፏን ታፍተለትላለች።
እስከዛሬ እጇን አይቼው አላውቅም። ከድምፅዋ በቀር ምኗንም አስተውዬ አላውቅም። ለምንድ ነበር አውርቻት የማላውቀው? ለምንድነው ግንባሬን እንደቋጠርኩ ገብቼ የምወጣው? እንዲያከብሩኝ? ሲሳይ እንዳለኝ በራሴ ስለማልተማመን? ወይስ ደረጃዬን ስጠብቅ?
“ሲስተር ቤተሰብ አለሽ እንዴ?” አልኳት ለመሄድ እየተሰናዳሁ
“አዎን ባለትዳር ነኝ። አንድ ልጅም አለኝ። ምነው? ምን አጠፋሁ?”
ጉልበቴ ከዳኝ። ዞሬ አየኋት። በደቂቃ ብዙ ነገር አሰብኩ። ትፈራኛለች ምክኒያቱም ስራዋን ማጣት አትፈልግም። ከስራ ውጪ ስለምንም ነገር አውርቻት አላውቅም።ደሜ ቀዘቀዘ። እንዴት አይነት ጭራቅ አድርገው ነው የሚያስቡኝ?
“እንዲሁ ማወቅ ፈልጌ ነው።ለምን ትፈሪኛለሽ? አንቺ በጣም ታታሪ ሰራተኛ ነሽ እኮ!!” ትከሻዋን ዳበስ አድርጌ ወጣሁ።
★ ★ ★
ፈገግ እያልኩ መሆኔ ለራሴ ይታወቀኛል። ታካሚዎቼን እየፈገግኩ እንደማዋራቸው ገብቶኛል እያፏጨሁም መሰለኝ።ሰሞኑን በተደጋጋሚ ከሲሳይ ጋር እራቴን መብላቴን ተከትሎ እንደዚያ እየሆንኩ ነው ዶክተር ሰይፈን ይቅርታ መጠየቄ የሆነ ጭነት ከላዬ ላይ እንደማራገፍ ነበር ወደ ስራ እንዲመለስ የሚያስፈልገውን ሁሉ እንደማደርግ ስነግረው ግን
«ይቅርብኝ» ካለው ቃል በላይ ከቃሉ ጋር ከንፈሩን ነክሶ የፈገገው ፈገግታ ራሴን ደጋግሜ እንድረግም አድርጎኛል
ሲስተር ቀለም በተረኛ ታካሚ ፈንታ ገባች
“ዶክተር ሰው ይፈልግሻል?”
“ሲሳይ ነው? ትንሽ ታገሰኝ በይውና ተረኛ ታካሚ
👍6😁1
አስገቢልኝ።” “ዶክተር ……… ባለቤትሽ ነው።”
⚫️ይቀጥላል⚫️
ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳችሁ Like👍👍 እያደረጋችሁ የኔ ምርጦች😘
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
⚫️ይቀጥላል⚫️
ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳችሁ Like👍👍 እያደረጋችሁ የኔ ምርጦች😘
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
#ፍቅር_ማለት_ውዴ
የህልሙ ዘራችን የዕውን ፍሬ አፍርቶ
ቆንጅየ ልጅ ወልደን እሱም፤
ፍቅር ሊማር አንደበት አውጥቶ ፤
ፍቅር ማለት..እማ? ብሎ ቢጠይቅሽ ፤
ይህንን ንገሪው ሳትፈሪ ሳይጨንቅሽ ፤
#ፍቅር_ማለት_ልጄ
የተራ ሆሄያት ባዶ ጥርቃሚ ፤
የሶስት ፊደል ጥምረት
የቀል ልቅምቃሚ ፤የደቂቃ ስሜት
ወይ ጊዜያዊ ጥቅም አይደለም ምስጢሩ፤
#መስጠት
#መስጠት
#መሰጠት .....በቃ ሁሌም #መስጠት
እናም ልጄ ይህ ነው የፍቅር ቀመሩ ፤
ብለሽ ንገሪልኝ እንዲገባው አርገሽ ፤
ፍቅርን ሠጥቶ፤ምላሽ እንዳይጠብቅ
በደንብ አስጠንቅቀሽ ፤
.......ደግሞም እንዲህ በይው.........
#ፍቅር_ማለት_ልጄ
በአንዲት ውብ ማሳ ውስጥ..
ከአረም ከቁጥቋጦ ፈፅሞ በራቀች ፤
ከአንድ ገበሬ እጅ..
በፅናት ተዘርታ በዕምነት የበቀለች ፤
........... .............ፍቅር ቡቃያ ነች ፤
የአለምን ሃይሎች አጣምሮ ያደላት ፤
የተንኮል ገሞራ .....
የሃሜት አውሎ ንፋስ ገፍትሮ ማይጥላት ፤
ገንዘብ ጎርፍ ሆኖ.....
ስሯን ቢያጥለቀልቅ ፈፅሞ ማይነቅላት ፤
#ፍቅር ቡቃያ ናት..........."
......ብለሽ ንገሪልኝ....
ግን ይህን ሁሉ ቃል ከአንደበትሽ ሰምቶ ፤
....ፍቅር ማለት እማ ????
ብሎ ከጠየቀሽ ሳይረዳው ቀርቶ ፤
....ይህንን ንገሪው
"ገበሬው አምላክ ነው ማሳዋ ልባችን ፤
ዘሩ የፍቅር ቃል ቡቃያው ልጃችን ፤
እንዲያውም እንዲያውም....
ከተራ ቃላት ጋር ምን አፈታተነን ፤
ፍቅር ማለት ውዴ!!!!
በቃ እኔና አንች ነን 💝
የህልሙ ዘራችን የዕውን ፍሬ አፍርቶ
ቆንጅየ ልጅ ወልደን እሱም፤
ፍቅር ሊማር አንደበት አውጥቶ ፤
ፍቅር ማለት..እማ? ብሎ ቢጠይቅሽ ፤
ይህንን ንገሪው ሳትፈሪ ሳይጨንቅሽ ፤
#ፍቅር_ማለት_ልጄ
የተራ ሆሄያት ባዶ ጥርቃሚ ፤
የሶስት ፊደል ጥምረት
የቀል ልቅምቃሚ ፤የደቂቃ ስሜት
ወይ ጊዜያዊ ጥቅም አይደለም ምስጢሩ፤
#መስጠት
#መስጠት
#መሰጠት .....በቃ ሁሌም #መስጠት
እናም ልጄ ይህ ነው የፍቅር ቀመሩ ፤
ብለሽ ንገሪልኝ እንዲገባው አርገሽ ፤
ፍቅርን ሠጥቶ፤ምላሽ እንዳይጠብቅ
በደንብ አስጠንቅቀሽ ፤
.......ደግሞም እንዲህ በይው.........
#ፍቅር_ማለት_ልጄ
በአንዲት ውብ ማሳ ውስጥ..
ከአረም ከቁጥቋጦ ፈፅሞ በራቀች ፤
ከአንድ ገበሬ እጅ..
በፅናት ተዘርታ በዕምነት የበቀለች ፤
........... .............ፍቅር ቡቃያ ነች ፤
የአለምን ሃይሎች አጣምሮ ያደላት ፤
የተንኮል ገሞራ .....
የሃሜት አውሎ ንፋስ ገፍትሮ ማይጥላት ፤
ገንዘብ ጎርፍ ሆኖ.....
ስሯን ቢያጥለቀልቅ ፈፅሞ ማይነቅላት ፤
#ፍቅር ቡቃያ ናት..........."
......ብለሽ ንገሪልኝ....
ግን ይህን ሁሉ ቃል ከአንደበትሽ ሰምቶ ፤
....ፍቅር ማለት እማ ????
ብሎ ከጠየቀሽ ሳይረዳው ቀርቶ ፤
....ይህንን ንገሪው
"ገበሬው አምላክ ነው ማሳዋ ልባችን ፤
ዘሩ የፍቅር ቃል ቡቃያው ልጃችን ፤
እንዲያውም እንዲያውም....
ከተራ ቃላት ጋር ምን አፈታተነን ፤
ፍቅር ማለት ውዴ!!!!
በቃ እኔና አንች ነን 💝
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_አስራ_ሶስት
:
✍ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ዶክተሯ ቃሏን ጠብቃ ከሀያ ደቂቃ ቡሃላ በአነስታኛ ብልቃጥ ሀመራዊ አይነት ዝልግልግ ፈሳሽ ይዛ በምጣት ያለምንም ንግግር መድሀኒቱን ከብልቃጥ ውስጥ በስሪንጅ በምጠጥ ከእናቴ ደምስር ጋር ከቴያያዘው የጉልኮስ የፕላስቲክ ከረጢት ውስጥ ጨመረችውና …እንዳአመጣጦ ምንም ሳትናገር ወጥታ ሄደች፡፡
እኔም ደንዝዤ ስለነበረ የምታርገውን በፅሞና ከመታዘብ በዘለለ አንደበቴን አላቅቄ ቃላት ማውጣት አልቻልኩም..ምን እየተፈጠረ ነው..?እውነት እንዳለችው ይህ መድሀኒት እናቴን ይፈውሳት ይሆን…..?ነው ወይስ እያሾፈችብኝ ይሆን…..?እንደዛማ ከሆነ በህይወቷ ወስናለች ማለት ነው፡፡እዛው የቢሮዋ ወንበር ላይ እንደተቀመጠች በእነዚህ መዳፎቼ አንገቷን ፈጥርቄ ፀጥ ነው የማደርጋት ፡፡….በውስጤ ዛትኩ
በተጋደምኩበት ይሄንን እና የመሳሰሉትን ግትልትል ሀሳቦች እያሰብኩ ሳይታወቀኝ እንቅልፍ ይዞኝ ጭልጥ ብሎ ነበር ለካ ፡፡አይፈረድብኝም የሶስት ሙሉ ቀን እንቅልፍ ነው ያለብኝ፡፡
‹‹…ፀጋ …የእኔ ልጅ››የሚለው ከገነት ከመላዕክት አንደበት የሚፈስ የሚመስል ጡዑም ዜማ ያለው የእናቴ የጥሪ ድምጽ ነበር ከእንቅልፌ የቀሰቀሰኝ… ደንግጬ ከተጋደምኩበት የሆስፒታል አልጋ በርግጌ በመውረድ ወለሉ ላይ እናቴ ፊት ለፊት ተገተርኩ
‹‹..አረ ተረጋጋ የእኔ ጌታ..››ጥርት ያለ ንፅህ የእናቴ ድምፅ..
ማመን አልቻልኩም፡፡በስነስርአት ትራስ እንኳን መንተራስ ሳያስፈልጋ ቁጭ ብላለች፡፡ምንም በበሽታ የመድከም ምልክት በፊቷ አይታይም፡፡
‹‹እማ ደህና ነሽ…..?ተሸለሽ…..?አሁን ምን ይሰማሻል..?››በጥያቄ አጣደፍኳት
‹‹ይሄው እንደምታየው በጣም ደህና እና ፍፅም ጤነኛ ሆኜ ነው የተነሳሁት፡፡ይገርምሀል ለሊ,ት ተኝቼ ጠይም መላዕክ መጥታ ከጭንቅላቴ አንስታ መላ አካላቴን ስትዳብሰኝ ነበር…እግዜያብሄር ያአንተ ፀሎት ሰምቶ ምሮኛል መሰለኝ፡፡››አለቺኝ በተፍለቀለቀ የደስታ ድምፀት
ተንጠራራውና አቀፍኳት ፡፡ግንባሯን …ጉንጮን …አፍንጫዋን እያፈራረቅኩ ሳምኳት ‹‹…አዎ እማ ድነሻል…እግዜያብሄር ይመስገን ተሳክቶልናል…ልጅቷ እንዳለችው ማድረግ ችላለች…ምትገርም ሴት ነች፡››
‹‹ስለማን ነው የምታወራው..?›› አለችኝ መቀባዠሬ ስላልገባት
‹‹አይ በህልሜ አየዋት ስላልሽው መላዕክ ነው ማወራው….ስላዳነችሽ መላአክ››አልኩና ርዕሱን አስቀየርኳት
‹‹አዎ እግዜር ነው የላከልኝ..ሄድ አሁን ሀኪም ጥራልኝ››
‹‹ምነው .. ..?የሚያምሽ ቦታ አለ እንዴ..?›› በድንጋጤ ጠየቅኳት
‹‹አረ በፍጽም… ይሄን ግሉኮስ ከላዬ እንዲነቅሉልኝ ነው…ሽንት ቤት መሄድ ፈልጋለው ›› ስትለኝ..ሮጬ ወጣውና በ10 ደቂቃ ውስጥ ተረኛውን ዶክተር አስከትዬ መጣው፡፡ይሄ ዶክተር እናቴ ሆስፒታል ከገባች ቀን ጀምሮ በዋናነት ስለጤናዋ ይከታተላት የነበረው ስለነበር እንዳያት ደነገጠ..በጣምም ግራ ተጋባ..ከግምቱ ውጭ የሆነ ሁኔታ ላይ ሆና ነው ያገኛት .
‹‹ማህሌት ምን ይሰማሻል. .?››
‹‹ፍጽም ጤነኝነት››
በጣም ጥሩ ..አሁን ወደቤት ከመሄድሽ በፊት ሙሉ ምርመራ ማድረግ አለብን ..››አለና ጉሉኮሱን ከእጇ ላይ በማለያየት ወጥቶ ሄደ …እኔም እሱ ለምርመራ ሚገለገልባቸውን መሳሪያዎች ይዞ እስኪመጣ ድረስ ስልኬን አወጣውና ለአያቴ ደወልኩለት…
‹‹ሄሎ አባ የት ነህ.?››
‹‹የት እሆናለው ልጄ… ቤተክርስቲያን ነኝ…ምነው ልጄ ባሰባት እንዴ .?›› ስብርብር ባለ ተስፋ የቆረጠ ደካማ ድምፅ ጠየቀኝ
‹‹አረ አባ ፍፅም ደህና ነች…ፀሎትህን ከጨረስክ ቀጥታ ወደሀስፒታል ና ››
‹‹አሟታል ማለት ነው ..መች አጣውት …እግዜያብሄር ዘንድሮ ሊያዋርደኝ ነው››አምላኩ ፊት መቆሙን እንኳን ዘንግቶ ተነጫነጨ
‹‹እወነቴን ነው አባ …ቆይ እንደውም…›› ብዬ ስልኩን ከጆሮዬ ላይ አነሳውና ለእናቴ አቀበልኳት ..የጠራ እና የነቃ ድምፆን በስልክ ከሰማ ቡሃላ በደስታ ሰክሮ እልልታውን ሲያቀልጠው በስልኩ ውስጥ ተሰማኝ…በዚህ እድሜው ልጁ ስትሞት አይቶ ባለመሳቀቁ ውስጤን ሀሴት ተሰማው …ቢያንስ ለጊዜው ይደሰት ..
እስከአራት ሰዓት መደረግ ያለበት ምርመራ ሁሉ ተደርጎላት ተጠናቀቀ..ውጤቱም ዶክተሮቹን በጣም ያስደመመ እና የበፊቱን የምርመራ ውጤት እንዲጠራጠሩ ያደረገ ነበር…እኔም ስለሆነው ነገር በውስጤ አፍኜ አብሬያቸው ከማደነቅ ውጭ ምንም ነገር ትንፍሽ ማለት አልቻልኩም…አልፈለኩምም፡፡
አዲሱ የህክምና ውጤት እንደሚያሳየው የእናቴ በሽታ ሙሉ በሙሉ የጠፋ ባይንም ደረጃው ግን 50 ፐርሰንት ወደኃላ የተመልሰል ነበር…ይህ ማለት ደግሞ ዋናው ሀኪምም እንዳረጋገጠልኝ በቅርብ ጊዜ ትሞታለች የሚለው ስጋት በአስተመማኝ ሁኔታ እንደተወገደ ነው፡፡
እንዴት እንደሆነ ባይገባኝም በእናቴ ላይ ተአምር ተፈፅሟል …ሙሴ የእስራኤልን ባህር በበትሩ ከፍሎ ወገኖቹን ያሻገራቸውን አይነተ ተአምር….አስራሁለት አመት ደም ሲፈሳት የነበረች ሴት የክርስቶስን የልብስ ጫፍ በእምነት ዳብሳ ከህመሞ ፈውስ ያገኘችበትን አይነት ተአምር ፡፡እርግጥ ታአምሩ ጅምር ነው…ምን አልባት በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ ሙሉ በሙሉ ልትፈወስና እኛንም ይበልጥ ልታስደምመን ትችል ይሆናል፡፡
በሰተመጨረሻ ለመሄድ ዝግጅታችንን እንዳጠናቀቅን ወደዋናው ዶክተር ቀረብኩና ‹‹አመሰግናለው ዶክተር..ሁላችሁንም እግዜር ይስጥልኝ አልኩ››
‹‹ኦኬ ..ያ ማለት ለህይወታችን መስጋት አይጠበቅብንም ማለት ነው..?››
‹‹ማለት . ..?አልገባኘም ..?››
‹‹እንደምትገለን በርግጠኘነት ዝተህብን ነበር…አሁን እናትህ በከፊልም ቢሆን በመዳኗ ለጊዜው የተረፍን ይመስለኛል››አለኝ ፈገግ እያለ
አንገቴን አቀረቀርኩ‹‹በጣም አዝናለው…እናቴ ለእኔ መላ ነገሬ ስለነበረች አብዝቼው ነበር…ያን ያህል ስለታገሳችሁኝ ውለታችሁን መቼም አረሳውም..››
‹‹አረ ስቀልድህ ነው..እኔም ሆንኩ ባለደረቦቼ በወቅቱ የነበርክበትን ሁኔታ በደንብ ስለተረዳን ምንም አይነት ቅሬታ እልተሰማንም …ነገሩን ያነሳውልህ እንዲሁ ልቀልድ ብዬ ነው ›አለኝ
እናቴን በጓደኛቼ በዘመድና በጎረቤት ሰዎች አሳጅቤ እባቴ ስንደርስ አምስት ሰዓት ሆኖ ነበር… እናቴን ወደጆሮዋ ተጠግቼ የምሄድበት ቦታ እንዳለና ልቆይ እንደምችል ነግሬት ከአጀብ ውስጥ ወጥቼ ወደሆስፒታል ተመለስኩ …ከተቻለ ዶክተሯን ለማግኘት ፤ ከለበላዛ እንዴት እዳማገኛትና ከዛም አልፎ ስለማንነቷ መረጃዎችን ከገኘው ለማጣራት…
ምክንያቱም ስለእሷ በአዕምሮዬ ውስጥ የሚጉላሉ ጥያቄዎች ከቁጥጥር ውጭ እያደረጉኝ እና መንፈሴን ክፉኛ እየረበሹት ነው.
1/ይቺ ዶክተር ማነች....?የትኛው ከተማ ወይም የትኛው ገጠር ተወልዳ የትኛው ዩኒቨርሲቲ ገብታ ተምራ እዴት እዚህ ተማድባ መጣች..?
2/እንዲህ አይነት ከሳይንስ አቅም በላይ የሆነ ህምምን ለመፈወስ የሚያስችል የባህል ህክምና ጥበብን በዚህ ዕድሜዋ እንዴት ልትካንበት ቻለች;..?››
3/በምን አይነት ተአምራዊ አጋጣሚ ሄስፒታሉ ለመስራት በተመደበች በመጀመሪያው ቀን የመጀመሪያዋ ታካሚዋ እናቴ ልትሆን ቻለች..?
2/ከእኔ እፈልገዋለው ያለችው በውለታዋ ምላሽ እንድከፍል የሚጠበቅብኝ ምንድነው....?ብር እንዳልሆነ እርግጠኛ ነኝ ፡፡አንገቷ ላይ ያጠለቀችው እባብ የመሰለ ጥምዝ ወርቅ እና ጆሮዋ ላይ ያንጠለጠለችው የከበረ ጌጥ የኑሮ ደረጃዋን ያሳብቅባታል፡፡የባህል መድሀኒት በሆስፒታል ቅጥር ግቢ በድብቅ እየቸረቸረች ገንዘብ የምትሰበስብ አይነት ሰው አይደለችም..አዎ በዛ እርግጠኛ ነኝ ፡፡ግን ምንም እንዳደርግላት ብትጠይቀኝ ግድ የለኝም…እራስህን አጥፋልኝ ብትለኝም አደርገዋለው…
:
#ክፍል_አስራ_ሶስት
:
✍ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ዶክተሯ ቃሏን ጠብቃ ከሀያ ደቂቃ ቡሃላ በአነስታኛ ብልቃጥ ሀመራዊ አይነት ዝልግልግ ፈሳሽ ይዛ በምጣት ያለምንም ንግግር መድሀኒቱን ከብልቃጥ ውስጥ በስሪንጅ በምጠጥ ከእናቴ ደምስር ጋር ከቴያያዘው የጉልኮስ የፕላስቲክ ከረጢት ውስጥ ጨመረችውና …እንዳአመጣጦ ምንም ሳትናገር ወጥታ ሄደች፡፡
እኔም ደንዝዤ ስለነበረ የምታርገውን በፅሞና ከመታዘብ በዘለለ አንደበቴን አላቅቄ ቃላት ማውጣት አልቻልኩም..ምን እየተፈጠረ ነው..?እውነት እንዳለችው ይህ መድሀኒት እናቴን ይፈውሳት ይሆን…..?ነው ወይስ እያሾፈችብኝ ይሆን…..?እንደዛማ ከሆነ በህይወቷ ወስናለች ማለት ነው፡፡እዛው የቢሮዋ ወንበር ላይ እንደተቀመጠች በእነዚህ መዳፎቼ አንገቷን ፈጥርቄ ፀጥ ነው የማደርጋት ፡፡….በውስጤ ዛትኩ
በተጋደምኩበት ይሄንን እና የመሳሰሉትን ግትልትል ሀሳቦች እያሰብኩ ሳይታወቀኝ እንቅልፍ ይዞኝ ጭልጥ ብሎ ነበር ለካ ፡፡አይፈረድብኝም የሶስት ሙሉ ቀን እንቅልፍ ነው ያለብኝ፡፡
‹‹…ፀጋ …የእኔ ልጅ››የሚለው ከገነት ከመላዕክት አንደበት የሚፈስ የሚመስል ጡዑም ዜማ ያለው የእናቴ የጥሪ ድምጽ ነበር ከእንቅልፌ የቀሰቀሰኝ… ደንግጬ ከተጋደምኩበት የሆስፒታል አልጋ በርግጌ በመውረድ ወለሉ ላይ እናቴ ፊት ለፊት ተገተርኩ
‹‹..አረ ተረጋጋ የእኔ ጌታ..››ጥርት ያለ ንፅህ የእናቴ ድምፅ..
ማመን አልቻልኩም፡፡በስነስርአት ትራስ እንኳን መንተራስ ሳያስፈልጋ ቁጭ ብላለች፡፡ምንም በበሽታ የመድከም ምልክት በፊቷ አይታይም፡፡
‹‹እማ ደህና ነሽ…..?ተሸለሽ…..?አሁን ምን ይሰማሻል..?››በጥያቄ አጣደፍኳት
‹‹ይሄው እንደምታየው በጣም ደህና እና ፍፅም ጤነኛ ሆኜ ነው የተነሳሁት፡፡ይገርምሀል ለሊ,ት ተኝቼ ጠይም መላዕክ መጥታ ከጭንቅላቴ አንስታ መላ አካላቴን ስትዳብሰኝ ነበር…እግዜያብሄር ያአንተ ፀሎት ሰምቶ ምሮኛል መሰለኝ፡፡››አለቺኝ በተፍለቀለቀ የደስታ ድምፀት
ተንጠራራውና አቀፍኳት ፡፡ግንባሯን …ጉንጮን …አፍንጫዋን እያፈራረቅኩ ሳምኳት ‹‹…አዎ እማ ድነሻል…እግዜያብሄር ይመስገን ተሳክቶልናል…ልጅቷ እንዳለችው ማድረግ ችላለች…ምትገርም ሴት ነች፡››
‹‹ስለማን ነው የምታወራው..?›› አለችኝ መቀባዠሬ ስላልገባት
‹‹አይ በህልሜ አየዋት ስላልሽው መላዕክ ነው ማወራው….ስላዳነችሽ መላአክ››አልኩና ርዕሱን አስቀየርኳት
‹‹አዎ እግዜር ነው የላከልኝ..ሄድ አሁን ሀኪም ጥራልኝ››
‹‹ምነው .. ..?የሚያምሽ ቦታ አለ እንዴ..?›› በድንጋጤ ጠየቅኳት
‹‹አረ በፍጽም… ይሄን ግሉኮስ ከላዬ እንዲነቅሉልኝ ነው…ሽንት ቤት መሄድ ፈልጋለው ›› ስትለኝ..ሮጬ ወጣውና በ10 ደቂቃ ውስጥ ተረኛውን ዶክተር አስከትዬ መጣው፡፡ይሄ ዶክተር እናቴ ሆስፒታል ከገባች ቀን ጀምሮ በዋናነት ስለጤናዋ ይከታተላት የነበረው ስለነበር እንዳያት ደነገጠ..በጣምም ግራ ተጋባ..ከግምቱ ውጭ የሆነ ሁኔታ ላይ ሆና ነው ያገኛት .
‹‹ማህሌት ምን ይሰማሻል. .?››
‹‹ፍጽም ጤነኝነት››
በጣም ጥሩ ..አሁን ወደቤት ከመሄድሽ በፊት ሙሉ ምርመራ ማድረግ አለብን ..››አለና ጉሉኮሱን ከእጇ ላይ በማለያየት ወጥቶ ሄደ …እኔም እሱ ለምርመራ ሚገለገልባቸውን መሳሪያዎች ይዞ እስኪመጣ ድረስ ስልኬን አወጣውና ለአያቴ ደወልኩለት…
‹‹ሄሎ አባ የት ነህ.?››
‹‹የት እሆናለው ልጄ… ቤተክርስቲያን ነኝ…ምነው ልጄ ባሰባት እንዴ .?›› ስብርብር ባለ ተስፋ የቆረጠ ደካማ ድምፅ ጠየቀኝ
‹‹አረ አባ ፍፅም ደህና ነች…ፀሎትህን ከጨረስክ ቀጥታ ወደሀስፒታል ና ››
‹‹አሟታል ማለት ነው ..መች አጣውት …እግዜያብሄር ዘንድሮ ሊያዋርደኝ ነው››አምላኩ ፊት መቆሙን እንኳን ዘንግቶ ተነጫነጨ
‹‹እወነቴን ነው አባ …ቆይ እንደውም…›› ብዬ ስልኩን ከጆሮዬ ላይ አነሳውና ለእናቴ አቀበልኳት ..የጠራ እና የነቃ ድምፆን በስልክ ከሰማ ቡሃላ በደስታ ሰክሮ እልልታውን ሲያቀልጠው በስልኩ ውስጥ ተሰማኝ…በዚህ እድሜው ልጁ ስትሞት አይቶ ባለመሳቀቁ ውስጤን ሀሴት ተሰማው …ቢያንስ ለጊዜው ይደሰት ..
እስከአራት ሰዓት መደረግ ያለበት ምርመራ ሁሉ ተደርጎላት ተጠናቀቀ..ውጤቱም ዶክተሮቹን በጣም ያስደመመ እና የበፊቱን የምርመራ ውጤት እንዲጠራጠሩ ያደረገ ነበር…እኔም ስለሆነው ነገር በውስጤ አፍኜ አብሬያቸው ከማደነቅ ውጭ ምንም ነገር ትንፍሽ ማለት አልቻልኩም…አልፈለኩምም፡፡
አዲሱ የህክምና ውጤት እንደሚያሳየው የእናቴ በሽታ ሙሉ በሙሉ የጠፋ ባይንም ደረጃው ግን 50 ፐርሰንት ወደኃላ የተመልሰል ነበር…ይህ ማለት ደግሞ ዋናው ሀኪምም እንዳረጋገጠልኝ በቅርብ ጊዜ ትሞታለች የሚለው ስጋት በአስተመማኝ ሁኔታ እንደተወገደ ነው፡፡
እንዴት እንደሆነ ባይገባኝም በእናቴ ላይ ተአምር ተፈፅሟል …ሙሴ የእስራኤልን ባህር በበትሩ ከፍሎ ወገኖቹን ያሻገራቸውን አይነተ ተአምር….አስራሁለት አመት ደም ሲፈሳት የነበረች ሴት የክርስቶስን የልብስ ጫፍ በእምነት ዳብሳ ከህመሞ ፈውስ ያገኘችበትን አይነት ተአምር ፡፡እርግጥ ታአምሩ ጅምር ነው…ምን አልባት በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ ሙሉ በሙሉ ልትፈወስና እኛንም ይበልጥ ልታስደምመን ትችል ይሆናል፡፡
በሰተመጨረሻ ለመሄድ ዝግጅታችንን እንዳጠናቀቅን ወደዋናው ዶክተር ቀረብኩና ‹‹አመሰግናለው ዶክተር..ሁላችሁንም እግዜር ይስጥልኝ አልኩ››
‹‹ኦኬ ..ያ ማለት ለህይወታችን መስጋት አይጠበቅብንም ማለት ነው..?››
‹‹ማለት . ..?አልገባኘም ..?››
‹‹እንደምትገለን በርግጠኘነት ዝተህብን ነበር…አሁን እናትህ በከፊልም ቢሆን በመዳኗ ለጊዜው የተረፍን ይመስለኛል››አለኝ ፈገግ እያለ
አንገቴን አቀረቀርኩ‹‹በጣም አዝናለው…እናቴ ለእኔ መላ ነገሬ ስለነበረች አብዝቼው ነበር…ያን ያህል ስለታገሳችሁኝ ውለታችሁን መቼም አረሳውም..››
‹‹አረ ስቀልድህ ነው..እኔም ሆንኩ ባለደረቦቼ በወቅቱ የነበርክበትን ሁኔታ በደንብ ስለተረዳን ምንም አይነት ቅሬታ እልተሰማንም …ነገሩን ያነሳውልህ እንዲሁ ልቀልድ ብዬ ነው ›አለኝ
እናቴን በጓደኛቼ በዘመድና በጎረቤት ሰዎች አሳጅቤ እባቴ ስንደርስ አምስት ሰዓት ሆኖ ነበር… እናቴን ወደጆሮዋ ተጠግቼ የምሄድበት ቦታ እንዳለና ልቆይ እንደምችል ነግሬት ከአጀብ ውስጥ ወጥቼ ወደሆስፒታል ተመለስኩ …ከተቻለ ዶክተሯን ለማግኘት ፤ ከለበላዛ እንዴት እዳማገኛትና ከዛም አልፎ ስለማንነቷ መረጃዎችን ከገኘው ለማጣራት…
ምክንያቱም ስለእሷ በአዕምሮዬ ውስጥ የሚጉላሉ ጥያቄዎች ከቁጥጥር ውጭ እያደረጉኝ እና መንፈሴን ክፉኛ እየረበሹት ነው.
1/ይቺ ዶክተር ማነች....?የትኛው ከተማ ወይም የትኛው ገጠር ተወልዳ የትኛው ዩኒቨርሲቲ ገብታ ተምራ እዴት እዚህ ተማድባ መጣች..?
2/እንዲህ አይነት ከሳይንስ አቅም በላይ የሆነ ህምምን ለመፈወስ የሚያስችል የባህል ህክምና ጥበብን በዚህ ዕድሜዋ እንዴት ልትካንበት ቻለች;..?››
3/በምን አይነት ተአምራዊ አጋጣሚ ሄስፒታሉ ለመስራት በተመደበች በመጀመሪያው ቀን የመጀመሪያዋ ታካሚዋ እናቴ ልትሆን ቻለች..?
2/ከእኔ እፈልገዋለው ያለችው በውለታዋ ምላሽ እንድከፍል የሚጠበቅብኝ ምንድነው....?ብር እንዳልሆነ እርግጠኛ ነኝ ፡፡አንገቷ ላይ ያጠለቀችው እባብ የመሰለ ጥምዝ ወርቅ እና ጆሮዋ ላይ ያንጠለጠለችው የከበረ ጌጥ የኑሮ ደረጃዋን ያሳብቅባታል፡፡የባህል መድሀኒት በሆስፒታል ቅጥር ግቢ በድብቅ እየቸረቸረች ገንዘብ የምትሰበስብ አይነት ሰው አይደለችም..አዎ በዛ እርግጠኛ ነኝ ፡፡ግን ምንም እንዳደርግላት ብትጠይቀኝ ግድ የለኝም…እራስህን አጥፋልኝ ብትለኝም አደርገዋለው…
👍5
ለእናቴ አንድ ተጨማሪ ቀን ለማግኘት የእኔን አንድ ሙሉ አመት ሰዋለው …
ቢሆነው እነዚህ እና ሌሎች ጥያቄዎቼን በቅደም ተከተል መልስ ሊያገኙ የሚችሉት በከፊል የሚያውቋት ሰዎች ሳገኝና ሳናግር ሙሉ በሙሉ ደግሞ በቀጥታ ከአሷ ተገናኝቼ ሳወራት ነው፡፡
እንዴት ግን ትናንትናውኑ ስልኳን ሳልጠይቅና ሳልቀበላት… .? ዳሩ በዛ ውድቅት ለሊት በሚሆኑት አስደማሚ ክስቶች ሁሉ እንደዛ ደንዝዤ ስልክ መቀበል እንዳለበኝ ብዘነጋ ብዙም የሚገርም አይደለም፡፡
.ሆስፒታል ስድስት ሰዓት ከመሆኑ በፊት ብደርስም ስለ አዲሷ ዶክተር እንደተመደበች ከማወቅ በዘለለ አብዛኞቹ ምን እንደምትመስል እኳን እስካአሁን በአካል አላዮትም …አስተዳደር ክፍል ገባውና ስልኳን እንዲሰጡኝ በግግምና ጠየቅኳቸው፡፡የግለሰብ የግል ስልክ ካለፍቃዱ ለማንም መስጠት እንደማይችሉ ነገሩኝ፡በስተመጨረሻ በመከራ ለምኜ በቢሮ ስልክ ደውለው ቀጥታ እንዲያገኛኙኝ አሳመንኮቸው… ደወሉላት፡፡
‹‹ሄሎ ዶክተር››
‹‹ሄሎ ጤና ይስጥልኝ…ማን ልበል፡፡››ጥርት ያለ ግን ደግሞ ያዛዥነት ተፅዕኖ ያለው ከባድ የሴት ድምፅ ከዛኛው ጫፍ ተሰማ…
‹‹አታውቂኝም ማለቴ….››ቃላትን በቀላሉ ሰካክቼ ከአንደበቴ በማውጣት ሀሰቤን መግለፅ አቃተኝ
‹‹ማለትህ የማታው ልጅ ነኝ…እናቴን አክመሽ ስላዳንሺልኝ ላመሰግንሽ ነው..፡፡ልትለኝ አይደል .?››
ለማለት ፈልጌ ማለት ያቃተኝን ቀጥታ ከአንደበቷ ስሰማ ቃላቶቼ ሁሉ አንደበቴ ውስጥ እየሞሙ ሲበተኑ ታወቀኝ
‹‹አዎ..ት..ክ..ክ.ል››
‹‹ተቀብያለው…››
‹‹እና ላገኝሽና በአካል ላመሰግንሽ ፈልጋለው፡፡››
‹‹ልታገኘኝ ባትፈልግም የግድ አገኘሀለው ….የማይሻር ውል አለን አይደል .?፡፡››
‹‹አዎ አረሳውትም››
‹‹ጎበዝ ልጅ …መርሳትም የለብህም …ለማንኛውም ስልክ ቁጥሬን ያዝ 09 13 303030 ነው…ደውልልኝ፡፡››
‹‹እሺ አመሰግናለው…እደውልልሻለው››ቅልስልስ ባለ ድምፅ
‹‹ቸው››ስልኩ ተጠረቀመ
እኔም የስልኩን እጃታ ቦታው መልሼ የተባበሩኝን ሰዎች በደመነፍሰ አመስግኜ እግሬን እየጎትትኩ የቢሮውንም የሆስፒታሉንም ቅጥር ግቢ ለቅቄ ወጣው፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
ቢሆነው እነዚህ እና ሌሎች ጥያቄዎቼን በቅደም ተከተል መልስ ሊያገኙ የሚችሉት በከፊል የሚያውቋት ሰዎች ሳገኝና ሳናግር ሙሉ በሙሉ ደግሞ በቀጥታ ከአሷ ተገናኝቼ ሳወራት ነው፡፡
እንዴት ግን ትናንትናውኑ ስልኳን ሳልጠይቅና ሳልቀበላት… .? ዳሩ በዛ ውድቅት ለሊት በሚሆኑት አስደማሚ ክስቶች ሁሉ እንደዛ ደንዝዤ ስልክ መቀበል እንዳለበኝ ብዘነጋ ብዙም የሚገርም አይደለም፡፡
.ሆስፒታል ስድስት ሰዓት ከመሆኑ በፊት ብደርስም ስለ አዲሷ ዶክተር እንደተመደበች ከማወቅ በዘለለ አብዛኞቹ ምን እንደምትመስል እኳን እስካአሁን በአካል አላዮትም …አስተዳደር ክፍል ገባውና ስልኳን እንዲሰጡኝ በግግምና ጠየቅኳቸው፡፡የግለሰብ የግል ስልክ ካለፍቃዱ ለማንም መስጠት እንደማይችሉ ነገሩኝ፡በስተመጨረሻ በመከራ ለምኜ በቢሮ ስልክ ደውለው ቀጥታ እንዲያገኛኙኝ አሳመንኮቸው… ደወሉላት፡፡
‹‹ሄሎ ዶክተር››
‹‹ሄሎ ጤና ይስጥልኝ…ማን ልበል፡፡››ጥርት ያለ ግን ደግሞ ያዛዥነት ተፅዕኖ ያለው ከባድ የሴት ድምፅ ከዛኛው ጫፍ ተሰማ…
‹‹አታውቂኝም ማለቴ….››ቃላትን በቀላሉ ሰካክቼ ከአንደበቴ በማውጣት ሀሰቤን መግለፅ አቃተኝ
‹‹ማለትህ የማታው ልጅ ነኝ…እናቴን አክመሽ ስላዳንሺልኝ ላመሰግንሽ ነው..፡፡ልትለኝ አይደል .?››
ለማለት ፈልጌ ማለት ያቃተኝን ቀጥታ ከአንደበቷ ስሰማ ቃላቶቼ ሁሉ አንደበቴ ውስጥ እየሞሙ ሲበተኑ ታወቀኝ
‹‹አዎ..ት..ክ..ክ.ል››
‹‹ተቀብያለው…››
‹‹እና ላገኝሽና በአካል ላመሰግንሽ ፈልጋለው፡፡››
‹‹ልታገኘኝ ባትፈልግም የግድ አገኘሀለው ….የማይሻር ውል አለን አይደል .?፡፡››
‹‹አዎ አረሳውትም››
‹‹ጎበዝ ልጅ …መርሳትም የለብህም …ለማንኛውም ስልክ ቁጥሬን ያዝ 09 13 303030 ነው…ደውልልኝ፡፡››
‹‹እሺ አመሰግናለው…እደውልልሻለው››ቅልስልስ ባለ ድምፅ
‹‹ቸው››ስልኩ ተጠረቀመ
እኔም የስልኩን እጃታ ቦታው መልሼ የተባበሩኝን ሰዎች በደመነፍሰ አመስግኜ እግሬን እየጎትትኩ የቢሮውንም የሆስፒታሉንም ቅጥር ግቢ ለቅቄ ወጣው፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3❤1
#ስንቴ_ገረዝኩት ✂️
:
#ክፍል_አራት (የመጨረሻ ክፍል)
:
:
✍ደረሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
....“ባለቤትሽ? ኢሳያስ?…………”
“ቢሮዬ ድረስ እየመጣህ ለምን ትረብሸኛለህ ኢሳ?”
“ናፈቅሽኝ!! ከዚህ በላይ ሳላይሽ መቆየት አልችልም።”
ከዩንቨርስቲ ጀምሮ የማውቀው ሰው ነው ኢሳያስ ። ለ6 ዓመት አብሮኝ የቆየ የትዳር አጋሬም ነው። አብረን በኖርንባቸው ጊዜያት መጀመሪያዎቹ አመታት በፍቅር ያጌጡ ነበሩ። እየሰነባበተ ግን ሳንጨቃጨቅ ያለፉ ቀናት ውስን ሆኑ። የሁለት ዓመት ልጃችን በሞት ስትለየን ሰላማችን ይብስ ደፈረሰ። ልጃችን የሞተችው በምግብ መመረዝ ነው። ታማ ስትሰቃይ ሁለታችንም ልንደርስላት አልቻልንም ነበር። ሰራተኛዋ ስትደውልልኝ ስራ ላይ ነበርኩ። ስልኬን እየሰማሁት ቆይቼ ለመደወል አስቤ ተውኩት። ግን ቆይቼም አልደወልኩም። ሌላ ስራ ያዝኩ። እናም ልጄን ሳልደርስላት ሞተች። እሱም በተመሳሳይ ምክንያት ስልክ ሳይመልስ ቀረ። ቆይቼ ስደርስ ዘግይቼ ነበር። ለዚህ በደሌ አንድ ሚሊየን ጊዜ ራሴን ብቀጣውም በቂ አይሆንም። ከኢሳያስ ጋር መወቃቀሱ አቁሳይ ስለነበር በሆነው ባልሆነው ሰበብ እየፈለጉ መነታረክ ሆነ ምሽታችን። ቤቱን ለቆ ከወጣ ሶስት ወር አለፈው።
“ቁጭ ብለን እንድናወራ እፈልጋለሁ።” አለኝ አይን አይኔን በልመና እያየ።
ምንድነው ልለው የነበረው? ‘ውጣልኝ‘ ነበር ሌላ ጊዜ ቢሆን የምለው። አሁን የምትሸሸዋን ሴት አይደለሁም። ምንም ቢሆን የምትጋፈጠዋን ማህደር እየተለማመድኳት ነው።
“እደውልልሃለሁ።” ያልኩትን ያመነኝ አይመስልም። ተገርሞ እያየኝ ተሰናብቶኝ ወጣ። የገባኝ አንድ ነገር ሲሳይ በብዙ ፍጥነት ማንነቴን እያሾረው መሆኑ ነው።
ወደ ቤቴ ገብቼ ሲሳይ ያለኝን አደረግኩ።
«በህይወትሽ የምትሸሺው ነገር ምንድነው? መስታወት ፊት ቁሚና ለራስሽ ንገሪው። እመኚው!! መቀየር የማትችዪውን ነገር መቀበል ነው የሚፈውሰው።» ነበር ያለኝ
የልጄን ፎቶዎች ከደበቅኩበት አወጣኋቸው። በመጀመሪያው ቀን ቀላል አይሆንም ነበር ያለኝ። ቀላል አልነበረም። ሁሉንም ፎቶዎች በፊት የተሰቀሉበት መለስኳቸው። መሸሽም መደበቅም መድሃኒት አይሆንም። ስሸሽ የተጠራቀመው እንባዬ ገደቡን ጥሶ አይኔን አደፈራረሰው። ስልኬ መጥራቱን እንኳን የሰማሁት ብዙ ከጠራ በኋላ ነበር።
«ምን ሆነሻል? አልቅሰሽ አይደለምኣ?» ሲሳይ ነው።
«ነው! አልቅሼ ነው።» እያልኩት ጭራሽ መንፈቅፈቅ ጀመርኩ።
«እህህህ ምን ተፈጠረ ቆይ?» እቤቴ ደጅ ድረስ አድርሶኝ ነበር የተመለሰው። መልስ መመለስ እስኪያቅተኝ ሲቃዬ አነቀኝ።
« በቃ በቃ እሺ መጣሁ። ስልኩን አትዝጊው እያወራሁሽ እደርስልሻለሁ። እኔ አጠገብሽ ሆኜ እንደፈለግሽ እንድታለቅሺ ፈቅድልሻለሁ። እስከዛ ግን ስወድሽ አታልቅሺ?» ብሎኝ ሊያስቀኝ እየሞከረ ከቤቱ ሲወጣ፤ «ብርድ እንዳይመታህ በደንብ ልበስ» ስለው «አትስጊ ካልሲ አጥልቄለታለሁ» ሲለኝ
ታክሲ ሲያናግር
«የኔ እመቤት ደሞ ስስ ፒጃማ ፍለጋ ቁምሳጥኑን ዘረጋግፊው አሉሽ!» ሲለኝ ሲከፍል
«ስንቴ መስታወት አየሽ?» ሲለኝ
ሲደርስ እውነትም ማልቀሴን ትቼ ልቤ ተሰቅሎ እየጠበቅኩት ነበር። በሩን ከፍቼ ተጠመጠምኩበት። ሙሽራውን በሰርጓ እለት ወደ መኝታ ቤታቸው እንደሚያስገባ ሙሽራ አቅፎኝ ወደሳሎኑ ገባ! ማልቀሴን እረሳሁት። ሳሎኑ ውስጥ የተሰቀለውን የእኔንና የኢሳያስን የሰርግ ፎቶ አይቶታል። ግን አልጠየቀኝም። ሌላ ነገር እያወራ ሲያስቀኝ ቆየ።
«ሲስ?»
«ወዬ እመቤቴ?»
«ስለእኔ ማወቅ ያለብህ ነገር አለ።»
«ምኑን ትነግሪኝ? በፎቶ አሳየሽኝኮ አስጎበኘሽኝ።» አለ ወደፎቶው እየጠቆመኝ።
«እየቀለድኩ አይደለም ሲስ! ከምሬ ነው።»
« እሺ እመቤቴ ንገሪኝ! ይኸው! Am all yours!»
ስለኢሳያስ እና ስለልጄ ነገርኩት ብቻዬን ስለፈልፍ ሲያባብለኝ እና ሲደባብሰኝ ብቻ ቆየ። ብዙ ደቂቃ እቅፉ ውስጥ ካቆየኝ በኋላ
« ባንቺ ደረጃ ካሉ ሴቶች ይልቅ አንዲት ምንም የማታውቅ የቤት እመቤት የሰመረ ትዳር ለምን የሚኖራት ይመስልሻል?» አለኝ
« ጭራሽ እንደዛ ስለመሆኑም እንጃልህ! ምን ለማለት ፈልገህ ነው?»
«ይሄ ሀቅ ነው ብዙ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት በጋራ ስምምነት ባስቀመጥነው ደረጃ ብዙዎቹ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ያሉ ሴቶች በትዳራቸው ስኬታማ አይደሉም።»
«ምናልባት ከትዳራቸው ሌላ ትኩረታቸውን የሚሻ ሌላ ስራ ስላላቸው?»
«እኔ አይመስለኝም። እነዛ በትዳር ውስጥ ለፍቅር ወይ ለልጃቸው አልያም በሌላ ምክንያት ዝቅ ማለትን ያውቁበታል። እስኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ? ክርስቶስ ለባል የሰጠው ትእዛዛ ሚስትህን ክርስቶስ ቤተክርስትያንን በወደደበት ፍቅር ውደድ የሚል ነው። ያ ማለት ነፍሱን እስከመስጠት። ለሚስት ያላት ግን ሚስት ለባሏ ትገዛ ነው። የቱ የሚከብድ ይመስልሻል?» ሳልመልስለት ራሱ ቀጠለ።
«ባትወጂም መገዛት ትችያለሽ። ወደሽ አለመገዛት ግን በፍፁም አትችዪም።» ዝም ነበር መልሴ። ከአንዱ ስሜት ወደሌላው መሻገር ምንም አይከብደውም። መከፋቴን አስረስቶኝ አመሸን።
«ያው እንደምታውቂው ድንግል ነኝ። በዛ ላይ ቁስሉ ራሱ ሰበብ አይፈልግም።» ብሎኝ እኩለ ለሊት አልፎ ወደ ቤቱ ሄደ።
★ ★ ★
በሚቀጥለው ቀን በስራ የደከመ ሰውነቴን እየጎተትኩ መኪናዬጋ ደረስኩ። መሽቷል። እቤቴ ገብቼ ማረፍ ነው ያማረኝ። ስልኬ ጠራ። ሲሳይ ነው።
“እራት በላሽ?”
“አልበላሁም። ግን ደክሞኛል በጣም።”
“እማ ቆንጆ እራት ነው የሰራችው። እየጠበቀችሽ ነው።”
“ትቀልዳለህ እንዴ? ማን ነኝ ብዬ ነው እናትህ ቤት እራት ልበላ የምመጣው?”
“ማንም መሆን አይጠበቅብሽም። ሰው መሆን የእማን እራት ለመብላት በቂ ነው።”
★ ★ ★
አመመኝ። የቤተሰቡ ፍቅር አሳመመኝ።
“ደህና ነሽ ግን?”
“ምነው ደስ አላለሽም?”
“ምነው ልጄ ከፋሽሳ?”
ይሉኛል እየተቀባበሉ ። አመመኝ። የሚታገለኝን እንባ እየዋጥኩ የደመቀ እራት በላሁ። የቤተሰብ ፍቅር ህመሜ፣ ንጭንጬ ፣ ሽንፈቴ፣ ድክመቴ……… መሆኑ አልገባቸውም። ይሄን ፍቅር በዘመኔ አይቼው አንጊንቼው እንደማላውቅ አያውቁም። የሲሳይ እናት ፊቴን እያገላበጡ፣ ፀጉሬን እየዳበሱ የሆንኩትን ሲጠይቁኝ እናት እንደማላውቅ አያውቁም። አባትየው እየደጋገሙ ‘ልጄ‘ ሲሉኝ። አይኑ ለማያይ ያአረጀ አያቴ እየተላላኩ እና ምርኩዝ ሆኜ እንዳደግኩ አልገባቸውም። እህቶቹ እግሬ ስር በርከክ እያሉ ‘ሲሳይ አስከፍቶሽ ነው? እሱ እኮ ክፍት አፍ ነው።” ሲሉኝ አያቴ ሞቶ የአክስቶቼ ልጆች እንደምናምንቴ እየቆጠሩኝ ተምሬ መጨረሴን አያውቁም። ብዙ አወሩኝ። እቤት ይዟት የመጣ ብቸኛ ሴት መሆኔን ነገሩኝ።
★ ★ ★
እንደምንም ያመቅኩትን እንባዬን መኪናዬ ውስጥ ሲሳይ እቅፍ ውስጥ ዘረገፍኩት። አላባበለኝም። እየደጋገመ እንባዬን እየጠረገ ፣ ፀጉሬን እያሻሸ ጠበቀኝ።
“አውሪኝ። የተሰማሽን ሁሉ አውሪኝ።” አለኝ። ሲቃዬ አላስወራ አለኝ።
ጣቶቹን ፀጉሬ ውስጥ ሰዶ ወደራሱ አስጠጋኝ። ይበልጥ ሲቀርበኝ ከመቃወም ይልቅ ልስመው ፈለግኩ። በሌላኛው እጁ እንባዬን ከጉንጬ ላይ ጠራረገው። ከንፈሩ ከንፈሬን የሚነካበት ሰዓት ረዘመብኝ። መጠበቅ አቃተኝ። ሳምኩት። ነፍስ በሚያሳርፍ መሳሙ ለደቂቃዎች ሳመኝ።
“ምንም ይሁን ንገሪኝ፣ አንድም ሳታስቀሪ የተሰማሽን ንገሪኝ፣ አንቺ ራስሽን ከምትረጂው በላይ እረዳሻለሁ። እንባሽ ከመጣ አልቅሺ ብቻ ልስማሽ!” አለኝ መረጋጋቴን ሲያይ
“አሁን እኮ መሽቷል። ሌላ ቀን ላውራህ?”
“ማደር ካለብኝ እየሰማሁሽ አድራለሁ።”
አውርቼ የማላውቃቸውን ብዙ ነገሮች ነገርኩት። ሳለቅስ አያባብለኝም። እጄን እየደባበሰ ይሰማኛል። ስለቤተሰቦቼ ሁሉንም ነገርኩት። አያቴ ሲሞት ከልጅነቴ ጀም
:
#ክፍል_አራት (የመጨረሻ ክፍል)
:
:
✍ደረሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
....“ባለቤትሽ? ኢሳያስ?…………”
“ቢሮዬ ድረስ እየመጣህ ለምን ትረብሸኛለህ ኢሳ?”
“ናፈቅሽኝ!! ከዚህ በላይ ሳላይሽ መቆየት አልችልም።”
ከዩንቨርስቲ ጀምሮ የማውቀው ሰው ነው ኢሳያስ ። ለ6 ዓመት አብሮኝ የቆየ የትዳር አጋሬም ነው። አብረን በኖርንባቸው ጊዜያት መጀመሪያዎቹ አመታት በፍቅር ያጌጡ ነበሩ። እየሰነባበተ ግን ሳንጨቃጨቅ ያለፉ ቀናት ውስን ሆኑ። የሁለት ዓመት ልጃችን በሞት ስትለየን ሰላማችን ይብስ ደፈረሰ። ልጃችን የሞተችው በምግብ መመረዝ ነው። ታማ ስትሰቃይ ሁለታችንም ልንደርስላት አልቻልንም ነበር። ሰራተኛዋ ስትደውልልኝ ስራ ላይ ነበርኩ። ስልኬን እየሰማሁት ቆይቼ ለመደወል አስቤ ተውኩት። ግን ቆይቼም አልደወልኩም። ሌላ ስራ ያዝኩ። እናም ልጄን ሳልደርስላት ሞተች። እሱም በተመሳሳይ ምክንያት ስልክ ሳይመልስ ቀረ። ቆይቼ ስደርስ ዘግይቼ ነበር። ለዚህ በደሌ አንድ ሚሊየን ጊዜ ራሴን ብቀጣውም በቂ አይሆንም። ከኢሳያስ ጋር መወቃቀሱ አቁሳይ ስለነበር በሆነው ባልሆነው ሰበብ እየፈለጉ መነታረክ ሆነ ምሽታችን። ቤቱን ለቆ ከወጣ ሶስት ወር አለፈው።
“ቁጭ ብለን እንድናወራ እፈልጋለሁ።” አለኝ አይን አይኔን በልመና እያየ።
ምንድነው ልለው የነበረው? ‘ውጣልኝ‘ ነበር ሌላ ጊዜ ቢሆን የምለው። አሁን የምትሸሸዋን ሴት አይደለሁም። ምንም ቢሆን የምትጋፈጠዋን ማህደር እየተለማመድኳት ነው።
“እደውልልሃለሁ።” ያልኩትን ያመነኝ አይመስልም። ተገርሞ እያየኝ ተሰናብቶኝ ወጣ። የገባኝ አንድ ነገር ሲሳይ በብዙ ፍጥነት ማንነቴን እያሾረው መሆኑ ነው።
ወደ ቤቴ ገብቼ ሲሳይ ያለኝን አደረግኩ።
«በህይወትሽ የምትሸሺው ነገር ምንድነው? መስታወት ፊት ቁሚና ለራስሽ ንገሪው። እመኚው!! መቀየር የማትችዪውን ነገር መቀበል ነው የሚፈውሰው።» ነበር ያለኝ
የልጄን ፎቶዎች ከደበቅኩበት አወጣኋቸው። በመጀመሪያው ቀን ቀላል አይሆንም ነበር ያለኝ። ቀላል አልነበረም። ሁሉንም ፎቶዎች በፊት የተሰቀሉበት መለስኳቸው። መሸሽም መደበቅም መድሃኒት አይሆንም። ስሸሽ የተጠራቀመው እንባዬ ገደቡን ጥሶ አይኔን አደፈራረሰው። ስልኬ መጥራቱን እንኳን የሰማሁት ብዙ ከጠራ በኋላ ነበር።
«ምን ሆነሻል? አልቅሰሽ አይደለምኣ?» ሲሳይ ነው።
«ነው! አልቅሼ ነው።» እያልኩት ጭራሽ መንፈቅፈቅ ጀመርኩ።
«እህህህ ምን ተፈጠረ ቆይ?» እቤቴ ደጅ ድረስ አድርሶኝ ነበር የተመለሰው። መልስ መመለስ እስኪያቅተኝ ሲቃዬ አነቀኝ።
« በቃ በቃ እሺ መጣሁ። ስልኩን አትዝጊው እያወራሁሽ እደርስልሻለሁ። እኔ አጠገብሽ ሆኜ እንደፈለግሽ እንድታለቅሺ ፈቅድልሻለሁ። እስከዛ ግን ስወድሽ አታልቅሺ?» ብሎኝ ሊያስቀኝ እየሞከረ ከቤቱ ሲወጣ፤ «ብርድ እንዳይመታህ በደንብ ልበስ» ስለው «አትስጊ ካልሲ አጥልቄለታለሁ» ሲለኝ
ታክሲ ሲያናግር
«የኔ እመቤት ደሞ ስስ ፒጃማ ፍለጋ ቁምሳጥኑን ዘረጋግፊው አሉሽ!» ሲለኝ ሲከፍል
«ስንቴ መስታወት አየሽ?» ሲለኝ
ሲደርስ እውነትም ማልቀሴን ትቼ ልቤ ተሰቅሎ እየጠበቅኩት ነበር። በሩን ከፍቼ ተጠመጠምኩበት። ሙሽራውን በሰርጓ እለት ወደ መኝታ ቤታቸው እንደሚያስገባ ሙሽራ አቅፎኝ ወደሳሎኑ ገባ! ማልቀሴን እረሳሁት። ሳሎኑ ውስጥ የተሰቀለውን የእኔንና የኢሳያስን የሰርግ ፎቶ አይቶታል። ግን አልጠየቀኝም። ሌላ ነገር እያወራ ሲያስቀኝ ቆየ።
«ሲስ?»
«ወዬ እመቤቴ?»
«ስለእኔ ማወቅ ያለብህ ነገር አለ።»
«ምኑን ትነግሪኝ? በፎቶ አሳየሽኝኮ አስጎበኘሽኝ።» አለ ወደፎቶው እየጠቆመኝ።
«እየቀለድኩ አይደለም ሲስ! ከምሬ ነው።»
« እሺ እመቤቴ ንገሪኝ! ይኸው! Am all yours!»
ስለኢሳያስ እና ስለልጄ ነገርኩት ብቻዬን ስለፈልፍ ሲያባብለኝ እና ሲደባብሰኝ ብቻ ቆየ። ብዙ ደቂቃ እቅፉ ውስጥ ካቆየኝ በኋላ
« ባንቺ ደረጃ ካሉ ሴቶች ይልቅ አንዲት ምንም የማታውቅ የቤት እመቤት የሰመረ ትዳር ለምን የሚኖራት ይመስልሻል?» አለኝ
« ጭራሽ እንደዛ ስለመሆኑም እንጃልህ! ምን ለማለት ፈልገህ ነው?»
«ይሄ ሀቅ ነው ብዙ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት በጋራ ስምምነት ባስቀመጥነው ደረጃ ብዙዎቹ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ያሉ ሴቶች በትዳራቸው ስኬታማ አይደሉም።»
«ምናልባት ከትዳራቸው ሌላ ትኩረታቸውን የሚሻ ሌላ ስራ ስላላቸው?»
«እኔ አይመስለኝም። እነዛ በትዳር ውስጥ ለፍቅር ወይ ለልጃቸው አልያም በሌላ ምክንያት ዝቅ ማለትን ያውቁበታል። እስኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ? ክርስቶስ ለባል የሰጠው ትእዛዛ ሚስትህን ክርስቶስ ቤተክርስትያንን በወደደበት ፍቅር ውደድ የሚል ነው። ያ ማለት ነፍሱን እስከመስጠት። ለሚስት ያላት ግን ሚስት ለባሏ ትገዛ ነው። የቱ የሚከብድ ይመስልሻል?» ሳልመልስለት ራሱ ቀጠለ።
«ባትወጂም መገዛት ትችያለሽ። ወደሽ አለመገዛት ግን በፍፁም አትችዪም።» ዝም ነበር መልሴ። ከአንዱ ስሜት ወደሌላው መሻገር ምንም አይከብደውም። መከፋቴን አስረስቶኝ አመሸን።
«ያው እንደምታውቂው ድንግል ነኝ። በዛ ላይ ቁስሉ ራሱ ሰበብ አይፈልግም።» ብሎኝ እኩለ ለሊት አልፎ ወደ ቤቱ ሄደ።
★ ★ ★
በሚቀጥለው ቀን በስራ የደከመ ሰውነቴን እየጎተትኩ መኪናዬጋ ደረስኩ። መሽቷል። እቤቴ ገብቼ ማረፍ ነው ያማረኝ። ስልኬ ጠራ። ሲሳይ ነው።
“እራት በላሽ?”
“አልበላሁም። ግን ደክሞኛል በጣም።”
“እማ ቆንጆ እራት ነው የሰራችው። እየጠበቀችሽ ነው።”
“ትቀልዳለህ እንዴ? ማን ነኝ ብዬ ነው እናትህ ቤት እራት ልበላ የምመጣው?”
“ማንም መሆን አይጠበቅብሽም። ሰው መሆን የእማን እራት ለመብላት በቂ ነው።”
★ ★ ★
አመመኝ። የቤተሰቡ ፍቅር አሳመመኝ።
“ደህና ነሽ ግን?”
“ምነው ደስ አላለሽም?”
“ምነው ልጄ ከፋሽሳ?”
ይሉኛል እየተቀባበሉ ። አመመኝ። የሚታገለኝን እንባ እየዋጥኩ የደመቀ እራት በላሁ። የቤተሰብ ፍቅር ህመሜ፣ ንጭንጬ ፣ ሽንፈቴ፣ ድክመቴ……… መሆኑ አልገባቸውም። ይሄን ፍቅር በዘመኔ አይቼው አንጊንቼው እንደማላውቅ አያውቁም። የሲሳይ እናት ፊቴን እያገላበጡ፣ ፀጉሬን እየዳበሱ የሆንኩትን ሲጠይቁኝ እናት እንደማላውቅ አያውቁም። አባትየው እየደጋገሙ ‘ልጄ‘ ሲሉኝ። አይኑ ለማያይ ያአረጀ አያቴ እየተላላኩ እና ምርኩዝ ሆኜ እንዳደግኩ አልገባቸውም። እህቶቹ እግሬ ስር በርከክ እያሉ ‘ሲሳይ አስከፍቶሽ ነው? እሱ እኮ ክፍት አፍ ነው።” ሲሉኝ አያቴ ሞቶ የአክስቶቼ ልጆች እንደምናምንቴ እየቆጠሩኝ ተምሬ መጨረሴን አያውቁም። ብዙ አወሩኝ። እቤት ይዟት የመጣ ብቸኛ ሴት መሆኔን ነገሩኝ።
★ ★ ★
እንደምንም ያመቅኩትን እንባዬን መኪናዬ ውስጥ ሲሳይ እቅፍ ውስጥ ዘረገፍኩት። አላባበለኝም። እየደጋገመ እንባዬን እየጠረገ ፣ ፀጉሬን እያሻሸ ጠበቀኝ።
“አውሪኝ። የተሰማሽን ሁሉ አውሪኝ።” አለኝ። ሲቃዬ አላስወራ አለኝ።
ጣቶቹን ፀጉሬ ውስጥ ሰዶ ወደራሱ አስጠጋኝ። ይበልጥ ሲቀርበኝ ከመቃወም ይልቅ ልስመው ፈለግኩ። በሌላኛው እጁ እንባዬን ከጉንጬ ላይ ጠራረገው። ከንፈሩ ከንፈሬን የሚነካበት ሰዓት ረዘመብኝ። መጠበቅ አቃተኝ። ሳምኩት። ነፍስ በሚያሳርፍ መሳሙ ለደቂቃዎች ሳመኝ።
“ምንም ይሁን ንገሪኝ፣ አንድም ሳታስቀሪ የተሰማሽን ንገሪኝ፣ አንቺ ራስሽን ከምትረጂው በላይ እረዳሻለሁ። እንባሽ ከመጣ አልቅሺ ብቻ ልስማሽ!” አለኝ መረጋጋቴን ሲያይ
“አሁን እኮ መሽቷል። ሌላ ቀን ላውራህ?”
“ማደር ካለብኝ እየሰማሁሽ አድራለሁ።”
አውርቼ የማላውቃቸውን ብዙ ነገሮች ነገርኩት። ሳለቅስ አያባብለኝም። እጄን እየደባበሰ ይሰማኛል። ስለቤተሰቦቼ ሁሉንም ነገርኩት። አያቴ ሲሞት ከልጅነቴ ጀም
👍11❤1
ምርኩዙ ሆኜ ስላደግኩ ያለውን ንብረት ሁሉ ተናዞልኝ ነበር የሞተው። በንብረቱ ሳቢያ ዘመዶቼ ሁሉ በፊት ይጠሉኝ ከነበረው በብዙ እጥፍ ጠሉኝ።
የደበቅኩት የለም ሁሉንም ነገርኩት። ያልሰማኝ የለም። ያለፍትን ውሳኔዎቼን በሙሉ ቆም ብዬ እንዳይ አደረገኝ። እቤቴ ስገባ እንደሌላው ቀን ኢሳያስ የሌለበት ወና ቤት አላስጠላኝም። አልጋዬ ላይ ጋደም ብዬ ከራሴ ጋር አወራሁ።
“በራስሽ መተማመን ካለብሽ ራስሽን እወቂው። ጠንካራ ጎንሽን እና ድክመትሽን ለዪ፣ ድክመትሽን በጠንካራው ነገርሽ ለመሸፈን አትሞክሪ፣ ተጋፈጪው ማሻሻል ያለብሽን አሻሽዪ፣ ያለፈ ቁስልሽን ተቀበዪው እመኚው እንጂ አትሽሺው።” ያለኝን የሲሳይ ንግግር አሰብኩት። ደስ ብሎኝ ተኛሁ።
★ ★ ★
በጠዋት ወደስራ ስገባ ሲስተር ቀለምን ቀድማኝ አገኘኋት ። ጠርቻት ለልጆቿ የሆነ ነገር እንድታደርግ የተወሰነ ገንዘብ ሰጠኋት። እጄን እያገላበጠች ስትስም እንባዋ ነካኝ። አቀፍኳት። እስከዛሬ ልረዳት ባለመቻሌ ራሴን ረገምኩት። እቤቷ ሄጄ ልጆቿን ላይላት ለሳምንቱ መጨረሻ ቀጥርያት ስራ ጀመርን።
በህይወቴ ከመቼውም ጊዜ በላይ ደስተኛ ነኝ። ግን ደግሞ መንታ መንገድ ላይም ነኝ። ሲሳይና ኢሳያስ!!
የብዙ ዓመት አለሁሽ ባዬ ግን በራሴ ትህምክትና ፍራቻ ያልተረዳሁት ኢሳያስ
ሳልነግረው የማስበው እና የሆንኩት የሚገባው ሲሳይ
መወሰን ነበረብኝ። ማናቸውንም መምረጥ ህመም አለው። ፈሪ ግን አይደለሁም። አልሸሽም።
★ ★ ★
ውሳኔዬን መጀመሪያ ለሲሳይ ማሳወቅ ፈለግኩና አገኘሁት። ነገርኩት።
“እርግጠኛ ነሽ?” አለኝ መጀመሪያ ግራ እየተጋባ
“አዎን። መቼም እንደዛሬ እርግጠኛ የሆንኩበት ውሳኔ የለም። ” መለስኩለት
“አሁን ነው የገረዝሽኝ። ያማል።” አለኝ ድምፁን ዝግ አድርጎ
“አዝናለሁ። አንተ በህይወቴ ፈጣሪ የላከልኝ መልዓክ ነህ። ባልጎዳህ በወደድኩ። ” አልመለሰልኝም። ግንባሬን ሳመኝ። ለመጀመሪያ ጊዜ ሲከፋው አየሁት። ሊሄድ መንገድ ከጀመረ በኋላ መለስ ብሎ እንዲህ አለኝ
“ኢሳያስን እድለኛ መሆኑን ንገሪው!!”
★ ★ ★አሁን ጨረስን።★ ★ ★
አስተያየትቶን በ @atronosebot አድርሱን
ድርሰቱስ ተመችቶአችኋል? አሳውቁን።
የደበቅኩት የለም ሁሉንም ነገርኩት። ያልሰማኝ የለም። ያለፍትን ውሳኔዎቼን በሙሉ ቆም ብዬ እንዳይ አደረገኝ። እቤቴ ስገባ እንደሌላው ቀን ኢሳያስ የሌለበት ወና ቤት አላስጠላኝም። አልጋዬ ላይ ጋደም ብዬ ከራሴ ጋር አወራሁ።
“በራስሽ መተማመን ካለብሽ ራስሽን እወቂው። ጠንካራ ጎንሽን እና ድክመትሽን ለዪ፣ ድክመትሽን በጠንካራው ነገርሽ ለመሸፈን አትሞክሪ፣ ተጋፈጪው ማሻሻል ያለብሽን አሻሽዪ፣ ያለፈ ቁስልሽን ተቀበዪው እመኚው እንጂ አትሽሺው።” ያለኝን የሲሳይ ንግግር አሰብኩት። ደስ ብሎኝ ተኛሁ።
★ ★ ★
በጠዋት ወደስራ ስገባ ሲስተር ቀለምን ቀድማኝ አገኘኋት ። ጠርቻት ለልጆቿ የሆነ ነገር እንድታደርግ የተወሰነ ገንዘብ ሰጠኋት። እጄን እያገላበጠች ስትስም እንባዋ ነካኝ። አቀፍኳት። እስከዛሬ ልረዳት ባለመቻሌ ራሴን ረገምኩት። እቤቷ ሄጄ ልጆቿን ላይላት ለሳምንቱ መጨረሻ ቀጥርያት ስራ ጀመርን።
በህይወቴ ከመቼውም ጊዜ በላይ ደስተኛ ነኝ። ግን ደግሞ መንታ መንገድ ላይም ነኝ። ሲሳይና ኢሳያስ!!
የብዙ ዓመት አለሁሽ ባዬ ግን በራሴ ትህምክትና ፍራቻ ያልተረዳሁት ኢሳያስ
ሳልነግረው የማስበው እና የሆንኩት የሚገባው ሲሳይ
መወሰን ነበረብኝ። ማናቸውንም መምረጥ ህመም አለው። ፈሪ ግን አይደለሁም። አልሸሽም።
★ ★ ★
ውሳኔዬን መጀመሪያ ለሲሳይ ማሳወቅ ፈለግኩና አገኘሁት። ነገርኩት።
“እርግጠኛ ነሽ?” አለኝ መጀመሪያ ግራ እየተጋባ
“አዎን። መቼም እንደዛሬ እርግጠኛ የሆንኩበት ውሳኔ የለም። ” መለስኩለት
“አሁን ነው የገረዝሽኝ። ያማል።” አለኝ ድምፁን ዝግ አድርጎ
“አዝናለሁ። አንተ በህይወቴ ፈጣሪ የላከልኝ መልዓክ ነህ። ባልጎዳህ በወደድኩ። ” አልመለሰልኝም። ግንባሬን ሳመኝ። ለመጀመሪያ ጊዜ ሲከፋው አየሁት። ሊሄድ መንገድ ከጀመረ በኋላ መለስ ብሎ እንዲህ አለኝ
“ኢሳያስን እድለኛ መሆኑን ንገሪው!!”
★ ★ ★አሁን ጨረስን።★ ★ ★
አስተያየትቶን በ @atronosebot አድርሱን
ድርሰቱስ ተመችቶአችኋል? አሳውቁን።
👍8
ተስፋዬን በሙሉ አንች ላይ ብጥልም
የወደፊት ህልሜን ባንች ብገነባም
ከፈጣሪ በታች አንችኑ ባመልክም
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
#ማነው_እንዲህ_ያለሽ?
"ህይወት ይቋረጣል ህላዌ አይቀጥልም"
ለአመታት ደክሜ
የፀነስኩት ፍቅር የቀመምኩት ቅማም
እንደ ባቢሎን ግንብ ባንድ ጊዜ ቢናድም
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ማነው እንዲህ ያለሽ?
"ህይወት ይቋረጣል ህላዌ አይቀጥልም"
ፀሃይ ብትገባ ሰማዩ ቢጨልም
ደስታ ከኔ ርቆ ሀዘን ቢከበኝም
ካንች ተነጥዬ ብቻዬን ብቀርም
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
የጨለመው ሌሊት
የወረሰኝ ፅልመት መገፈፉ አይቀርም
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
የዳመነው ሰማይ የወረደብኝ ዶፍ
የጣለው በረዶ ያጥለቀለቀኝ ጎርፍ
ይዘገያል እንጅ ማባራቱ አይቀርም
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
#እውነቱን_ልንገርሽ?
እናልሽ የኔ አለም
ሌላ ህላዌ አለ ህይወት አትቆምም።
የወደፊት ህልሜን ባንች ብገነባም
ከፈጣሪ በታች አንችኑ ባመልክም
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
#ማነው_እንዲህ_ያለሽ?
"ህይወት ይቋረጣል ህላዌ አይቀጥልም"
ለአመታት ደክሜ
የፀነስኩት ፍቅር የቀመምኩት ቅማም
እንደ ባቢሎን ግንብ ባንድ ጊዜ ቢናድም
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
ማነው እንዲህ ያለሽ?
"ህይወት ይቋረጣል ህላዌ አይቀጥልም"
ፀሃይ ብትገባ ሰማዩ ቢጨልም
ደስታ ከኔ ርቆ ሀዘን ቢከበኝም
ካንች ተነጥዬ ብቻዬን ብቀርም
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
የጨለመው ሌሊት
የወረሰኝ ፅልመት መገፈፉ አይቀርም
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
የዳመነው ሰማይ የወረደብኝ ዶፍ
የጣለው በረዶ ያጥለቀለቀኝ ጎርፍ
ይዘገያል እንጅ ማባራቱ አይቀርም
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧
#እውነቱን_ልንገርሽ?
እናልሽ የኔ አለም
ሌላ ህላዌ አለ ህይወት አትቆምም።
👍2
#ቂም_የሸፈነው_እውነት
:
#ክፍል_አንድ
:
✍ደራሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
:
“መለያየት እፈልጋለሁ። ፍታኝ?” አልኩት በመኪናው መስኮት አሻግሬ ዓይኖቹን እየሸሸሁ።
“እሺ!!” ነበር መልሱ:: ቢያንስ ‘ለምን?’ ብሎ እንዴት አይጠይቀኝም?
“መች ነው እንዲሆን የምትፈልጊው? አሁን? ነገ? ከሳምንት በኋላ? መቼ?” ቀለል አድርጎ ቀጠለ። ቀጥዬ የምለው ጠፋኝ። ለራሴ ምክንያት መስጠት እፈልጋለሁ። ተናዶ እንዲናገረኝ እሱ ላይ እንከን ማግኘት አጥብቄ እፈልጋለሁ።’ፈታችው’ ከመባል ሌላ ቅጥያ ተጨምሮበት ‘ስላናደዳት ፈታችው’፣ ‘ስለመታት ፈታችው’……… ብቻ ምክንያቱ ከሱ ቢመጣ ደስ ይለኛል።
“ካለቀልን ዛሬም ብንፋታ ደስ ይለኛል።”
“ከዛሬ በኋላ ተፋተናል። የግድ በህግ መፋታት የለብንም። እኔን መፍታት አይደል የፈለግሽው? ስለወደድኩሽ እንጂ ማንም ስለፈረመ እና ምስክር ስለተጠራ አላገባሁሽም።” ብሎኝ ከመኪናው ወረደ እና የኔን በር ከፈተልኝ። ቤታችን ደጅ ደርሰን ነበር። ተናደድኩ።
“የንብረት ክፍፍሉ……..” አላስጨረሰኝም።
“የትኛውን ንብረት ነው የምትፈልጊው?” የአጥሩን በር ከፍቶ በእጁ እንድገባ አሳየኝ።
“ድርሻዬን::”
“ህምምምም…….. ቅር ካላለሽ ትንሿን መኪና ልውሰዳት ሌላውን ንብረት አልፈልገውም። ከዛሬ በኋላ ባልሽ አይደለሁም። ምንም ንብረትም የለኝም።” ብሎኝ ‘ትንሿ’ ያላት መኪናው ውስጥ ገብቶ ተመልሶ ሄደ።
ምን እንደምፈልግ ግራ ገባኝ። ካሳሁንን ሳላገባው በፊት ነበር የምፈታው ቀን የሚናፍቀኝ። ሳላገባው ፈትቼዋለሁ። እሱ ያገባኝ የመሰለው ቀን እኔ አግብቼም ፈትቼዋለሁ።ታዲያ ለምን አገባሁት? እሱን አላገባሁትም። ገንዘቡን እንጂ። ወንዶች ‘ሴት ልጅ ገንዘብ ያለው ወንድ ትወዳለች’ ሲሉ ሳቄ ያመልጠኛል። ወይ ሰውየው ማርኳታል ወይ ገንዘቡ ማርኳታል። ለአንዳቸው ቅድሚያ ትሰጣለች።ለገንዘቡ ብላ ከሆነ ገንዘቡን እንጂ እሱን አትወደውም። ገንዘቡ እስካለ ወይም የምትፈልገውን እስክታገኝ ድረስ አለች። እነሱ ግን ራሳቸውን ሳይሆን ገንዘባቸውን ያቀርቡላታል። ምክንያቱም የቁስን ያህል ራሳቸውን አያምኑትም። ስለዚህ ከቁሳቸው ይልቅ ራሳቸውን ተወዳጅ አድርገው ማቅረብ ሲሳናቸው ለገንዘቤ ብላ ነው የወደደችኝ ይላሉ እንጂ ገንዘቤን ነው የወደደችው አይሉም። ሰውየውን ከወደደችው ለገንዘቡ ብላ፣ ለቁመናው ብላ፣ ለወዙ ብላ…. የሚሉት ቀልድ አይጥመኝም። በቃ ሰውየውን ነው የወደደችው።
የዛን ቀን ምሽት አልመጣም። ጠበቅኩት። እውነቱን እንደሆነ ገባኝ። ካሳሁን ፈቶኛል። ሁለተኛው ቀን መሸ ።አልመጣም። አልደወለም። ሶስተኛ ቀን ሆነ……… አራተኛ ቀን መጣ… … አስር ቀን ሞላው። አልመጣምም። አልደወለምም። የገባኝ ግን ቢመጣ ደስ እንደሚለኝ ነው።እሱን መፍታት ያስደስተኛል ብዬ ያሰብኩትን ያህል አልነበረም የደስታዬ መጠን።
“አልወደውም። ከሀብቱ እንጂ ከእርሱ ጉዳይ የለኝም።” ለራሴ ብቻዬን አነበነብኩ። ስልኬን እልፍ ጊዜ ልደውልለት አነሳሁ። እልፍ ጊዜ ተውኩት። በአስራአንደኛው ቀን ስልኬ ጠራ። እሱ ነበረ። ለምን ደስ አለኝ? አብሬው መኖር የማልፈልገው ሰው ድምፁን መስማቴ እንዴት አስደሰተኝ?
“ደህና አደርሽ ሰብሊ? …… ላግኝሽ?”
“እሺ:: የት እንገናኝ?”
“ስራ ቦታ:: አራት ሰዓት ላይ መጥቼ ወስድሻለሁ።”
ስራ የመግባት ፍላጎት አልነበረኝም።ቁምሳጥኑን ከፍቼ ሊያቆነጀኝ ይችላል ብዬ ያሰብኩትን ሁሉ ልብስ ሞከርኩ። ላማልለው? ወይስ ከሱ በመለየቴ አለመከፋቴን ለማሳየት? ለራሴ የምሰጠው ምክንያት ባይኖረኝም በሱ ፊት ቆንጆ ሆኜ መታየት ፈለግኩኝ። አምስት ዓመት በትዳር አብሬው ስኖር ይሄ ግድ ሰጥቶኝ አያውቅም ነበር። በጥንቃቄ ስዋብ ብዙ ሰዓት ፈጅቼ ደረስኩ። ተጋብተን ብዙም ሳንቆይ ነበር ካሳሁን እቤት ከምትውዪ ብሎ ለንግድ ተስማሚ የሆነ ቦታ ላይ ትልቅ የሴቶች ፀጉር ቤት የከፈተልኝ ። በሩ ላይ ሲደርስ የት ይዞኝ ሊሄድ እንደሆነ እያሰብኩ ነበር። ብዙም ግድ ያልሰጠው ሰላምታ ሰጥቶኝ የመኪናውን በር ከፍቶ አስገባኝ። በሚከብድ ዝምታ መኪናውን መንዳት ጀመረ። ላገኘው እንዳልቸኮልኩ። ተጨነቅኩኝ።
“የት ነው የምንሄደው?” አፌ ይሄን ይበል እንጂ የትም ብንሄድ ግድ አልነበረኝም።
“የምንጨርሰው ጉዳይ አለን።”
ባንክ ቤት በር ጋ ስንደርስ በሁለታችን ስም የነበረውን የባንክ አካውንት ሊያዛውርልኝ መሆኑን ነገረኝ። በተዘባረቀ ስሜት ውስጥ ሆኜ የሚጠበቅብኝን ፈፀምኩ። እድሜውን ሙሉ የሰራው ገንዘብ መሆኑን እያወቅኩ ‘አንተስ?’ ብዬ እንኳን አልጠየቅኩትም። ነገር ዓለሙ ዞረብኝ። ምንም ሳንነጋገር ፀጉር ቤቱ በር ጋር ደርሰን።በር ሊከፍትልኝ ከመድረሱ ዘልዬ ከመኪናው ወረድኩ። በሌላ ትህትናው መቁሰል አልፈለኩም።
“የት ነው ያለኸው?” አልኩት
“ቤት እስካገኝ ሆቴል ነው ያረፍኩት::”
“ለጊዜው እኮ እቤት መሆን ትችላህ::”
“በሚቀጥለው ሳምንት በአንዱ ቀን የቤት ባለቤትነቱን ስም አዛውርልሻለሁ:: ሰሞኑን ስራ ስለሚበዛብኝ የምችል አይመስለኝም።” ብሎኝ መኪናው ውስጥ ገብቶ ሄደ። ራሴ የሚፈነዳ መሰለኝ።የማብድ የማብድ መስሎ ተሰማኝ። ወደቤቴ ሄድኩ።
የደስታዬ ጫፍ ይሆናል ብዬ የማስበው ቀን ሲመጣ እርካታን ሳይሆን ባዶነትን ተሸክሞ ነው የመጣው። የምፈልገው ሁሉ ኖረኝ።የማስበው ሁሉ ሰመረልኝ። ግን ትርጉም አልባ፣ ደስታ የለሽ ሙት ሆነብኝ።
**********
እንደማንም ያልነበረው ልጅነቴ፡-
ሰዎች ስለልጅነታቸው ሲያወሩ ‘እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ…..’ ሲሉ እገረማለሁ:: ‘ማንኛውም ኢትዮጵያዊ’ እኔን ያቀፈ ማዕቀፍ ይሆንን?
በቀን አንዴ ትርፍራፊ ለመቅመስ መስገብገብ፣ ጎዳና ላይ በገነባቻት የላስቲክ ቤት አጠገብ ተቀምጣ የምትለምን ወፈፍ የሚያደርጋት እናት፣መለመኛ የሆኑ መንታ ታናናሽ እህትና ወንድም፣ አስር ሳንቲም ለመመፅወት የሚመፃደቅ ሂያጅ፣ በባዶ እግርና በእኮዮች ምፀት ታጅቤ የምዳክርበት ትምህርት ቤት…….. ከማንኛውም ኢትዮጵያዊ የተለየ ልጅነት ነው።
ማንኛውም ኢትዮጵያዊ እናቱ ልመናን ተናዛለት አባት አልባ ህፃናት መንገድ ዳር አስታቅፋው አልሞተችም።
ማንኛውም ኢትዮጵያዊ እናቱ የሚበር መኪና ውስጥ ገብታ ስትሞት የሚሰማውን ከእብደት ያልተለየ ስሜት አያውቀውም።
የኔ ልጅነት ‘እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ’ የሚባለው ማዕቀፍ ውስጥ የማይገባው ልጅነት የሚባለው ዘመኔ በአስር ዓመቴ አክትሞ የሁለት አመት ጨቅላ መንታ ታናናሾቼን እየለመንኩ ማሳደግ ግዴታዬ ስለነበር ነው። ዓለም ስትከረፋብኝ፣ በርሃብ ከሚጮሁ ታናናሾቼ ጋር ኡኡኡ ብዬ ሳለቅስ “እንደእናቷ ጠሸሸች” እተባልኩ አራት ዓመታትን ጎዳና መግፋቴ ነበር።
አንድ ምሽት ታናናሾቼን አስተኝቼ ነትቦ እርቃኔን ያጋለጠውን ልብሴን እየሳብኩ ከላስቲክ ጎጆአችን ፊት ለፊት ቆሚያለሁ። መኪና ሲጢጥ ብሎ ሲቆም ሰማሁ። የሰከረ ወንድ ድምፅ ተከትሎ ተሰማኝ።
“እሙዬ ነይ እስኪ……”
🌑ይቀጥላል➡️
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ የኔ ምርጦች
አመሰግናለው
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_አንድ
:
✍ደራሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
:
“መለያየት እፈልጋለሁ። ፍታኝ?” አልኩት በመኪናው መስኮት አሻግሬ ዓይኖቹን እየሸሸሁ።
“እሺ!!” ነበር መልሱ:: ቢያንስ ‘ለምን?’ ብሎ እንዴት አይጠይቀኝም?
“መች ነው እንዲሆን የምትፈልጊው? አሁን? ነገ? ከሳምንት በኋላ? መቼ?” ቀለል አድርጎ ቀጠለ። ቀጥዬ የምለው ጠፋኝ። ለራሴ ምክንያት መስጠት እፈልጋለሁ። ተናዶ እንዲናገረኝ እሱ ላይ እንከን ማግኘት አጥብቄ እፈልጋለሁ።’ፈታችው’ ከመባል ሌላ ቅጥያ ተጨምሮበት ‘ስላናደዳት ፈታችው’፣ ‘ስለመታት ፈታችው’……… ብቻ ምክንያቱ ከሱ ቢመጣ ደስ ይለኛል።
“ካለቀልን ዛሬም ብንፋታ ደስ ይለኛል።”
“ከዛሬ በኋላ ተፋተናል። የግድ በህግ መፋታት የለብንም። እኔን መፍታት አይደል የፈለግሽው? ስለወደድኩሽ እንጂ ማንም ስለፈረመ እና ምስክር ስለተጠራ አላገባሁሽም።” ብሎኝ ከመኪናው ወረደ እና የኔን በር ከፈተልኝ። ቤታችን ደጅ ደርሰን ነበር። ተናደድኩ።
“የንብረት ክፍፍሉ……..” አላስጨረሰኝም።
“የትኛውን ንብረት ነው የምትፈልጊው?” የአጥሩን በር ከፍቶ በእጁ እንድገባ አሳየኝ።
“ድርሻዬን::”
“ህምምምም…….. ቅር ካላለሽ ትንሿን መኪና ልውሰዳት ሌላውን ንብረት አልፈልገውም። ከዛሬ በኋላ ባልሽ አይደለሁም። ምንም ንብረትም የለኝም።” ብሎኝ ‘ትንሿ’ ያላት መኪናው ውስጥ ገብቶ ተመልሶ ሄደ።
ምን እንደምፈልግ ግራ ገባኝ። ካሳሁንን ሳላገባው በፊት ነበር የምፈታው ቀን የሚናፍቀኝ። ሳላገባው ፈትቼዋለሁ። እሱ ያገባኝ የመሰለው ቀን እኔ አግብቼም ፈትቼዋለሁ።ታዲያ ለምን አገባሁት? እሱን አላገባሁትም። ገንዘቡን እንጂ። ወንዶች ‘ሴት ልጅ ገንዘብ ያለው ወንድ ትወዳለች’ ሲሉ ሳቄ ያመልጠኛል። ወይ ሰውየው ማርኳታል ወይ ገንዘቡ ማርኳታል። ለአንዳቸው ቅድሚያ ትሰጣለች።ለገንዘቡ ብላ ከሆነ ገንዘቡን እንጂ እሱን አትወደውም። ገንዘቡ እስካለ ወይም የምትፈልገውን እስክታገኝ ድረስ አለች። እነሱ ግን ራሳቸውን ሳይሆን ገንዘባቸውን ያቀርቡላታል። ምክንያቱም የቁስን ያህል ራሳቸውን አያምኑትም። ስለዚህ ከቁሳቸው ይልቅ ራሳቸውን ተወዳጅ አድርገው ማቅረብ ሲሳናቸው ለገንዘቤ ብላ ነው የወደደችኝ ይላሉ እንጂ ገንዘቤን ነው የወደደችው አይሉም። ሰውየውን ከወደደችው ለገንዘቡ ብላ፣ ለቁመናው ብላ፣ ለወዙ ብላ…. የሚሉት ቀልድ አይጥመኝም። በቃ ሰውየውን ነው የወደደችው።
የዛን ቀን ምሽት አልመጣም። ጠበቅኩት። እውነቱን እንደሆነ ገባኝ። ካሳሁን ፈቶኛል። ሁለተኛው ቀን መሸ ።አልመጣም። አልደወለም። ሶስተኛ ቀን ሆነ……… አራተኛ ቀን መጣ… … አስር ቀን ሞላው። አልመጣምም። አልደወለምም። የገባኝ ግን ቢመጣ ደስ እንደሚለኝ ነው።እሱን መፍታት ያስደስተኛል ብዬ ያሰብኩትን ያህል አልነበረም የደስታዬ መጠን።
“አልወደውም። ከሀብቱ እንጂ ከእርሱ ጉዳይ የለኝም።” ለራሴ ብቻዬን አነበነብኩ። ስልኬን እልፍ ጊዜ ልደውልለት አነሳሁ። እልፍ ጊዜ ተውኩት። በአስራአንደኛው ቀን ስልኬ ጠራ። እሱ ነበረ። ለምን ደስ አለኝ? አብሬው መኖር የማልፈልገው ሰው ድምፁን መስማቴ እንዴት አስደሰተኝ?
“ደህና አደርሽ ሰብሊ? …… ላግኝሽ?”
“እሺ:: የት እንገናኝ?”
“ስራ ቦታ:: አራት ሰዓት ላይ መጥቼ ወስድሻለሁ።”
ስራ የመግባት ፍላጎት አልነበረኝም።ቁምሳጥኑን ከፍቼ ሊያቆነጀኝ ይችላል ብዬ ያሰብኩትን ሁሉ ልብስ ሞከርኩ። ላማልለው? ወይስ ከሱ በመለየቴ አለመከፋቴን ለማሳየት? ለራሴ የምሰጠው ምክንያት ባይኖረኝም በሱ ፊት ቆንጆ ሆኜ መታየት ፈለግኩኝ። አምስት ዓመት በትዳር አብሬው ስኖር ይሄ ግድ ሰጥቶኝ አያውቅም ነበር። በጥንቃቄ ስዋብ ብዙ ሰዓት ፈጅቼ ደረስኩ። ተጋብተን ብዙም ሳንቆይ ነበር ካሳሁን እቤት ከምትውዪ ብሎ ለንግድ ተስማሚ የሆነ ቦታ ላይ ትልቅ የሴቶች ፀጉር ቤት የከፈተልኝ ። በሩ ላይ ሲደርስ የት ይዞኝ ሊሄድ እንደሆነ እያሰብኩ ነበር። ብዙም ግድ ያልሰጠው ሰላምታ ሰጥቶኝ የመኪናውን በር ከፍቶ አስገባኝ። በሚከብድ ዝምታ መኪናውን መንዳት ጀመረ። ላገኘው እንዳልቸኮልኩ። ተጨነቅኩኝ።
“የት ነው የምንሄደው?” አፌ ይሄን ይበል እንጂ የትም ብንሄድ ግድ አልነበረኝም።
“የምንጨርሰው ጉዳይ አለን።”
ባንክ ቤት በር ጋ ስንደርስ በሁለታችን ስም የነበረውን የባንክ አካውንት ሊያዛውርልኝ መሆኑን ነገረኝ። በተዘባረቀ ስሜት ውስጥ ሆኜ የሚጠበቅብኝን ፈፀምኩ። እድሜውን ሙሉ የሰራው ገንዘብ መሆኑን እያወቅኩ ‘አንተስ?’ ብዬ እንኳን አልጠየቅኩትም። ነገር ዓለሙ ዞረብኝ። ምንም ሳንነጋገር ፀጉር ቤቱ በር ጋር ደርሰን።በር ሊከፍትልኝ ከመድረሱ ዘልዬ ከመኪናው ወረድኩ። በሌላ ትህትናው መቁሰል አልፈለኩም።
“የት ነው ያለኸው?” አልኩት
“ቤት እስካገኝ ሆቴል ነው ያረፍኩት::”
“ለጊዜው እኮ እቤት መሆን ትችላህ::”
“በሚቀጥለው ሳምንት በአንዱ ቀን የቤት ባለቤትነቱን ስም አዛውርልሻለሁ:: ሰሞኑን ስራ ስለሚበዛብኝ የምችል አይመስለኝም።” ብሎኝ መኪናው ውስጥ ገብቶ ሄደ። ራሴ የሚፈነዳ መሰለኝ።የማብድ የማብድ መስሎ ተሰማኝ። ወደቤቴ ሄድኩ።
የደስታዬ ጫፍ ይሆናል ብዬ የማስበው ቀን ሲመጣ እርካታን ሳይሆን ባዶነትን ተሸክሞ ነው የመጣው። የምፈልገው ሁሉ ኖረኝ።የማስበው ሁሉ ሰመረልኝ። ግን ትርጉም አልባ፣ ደስታ የለሽ ሙት ሆነብኝ።
**********
እንደማንም ያልነበረው ልጅነቴ፡-
ሰዎች ስለልጅነታቸው ሲያወሩ ‘እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ…..’ ሲሉ እገረማለሁ:: ‘ማንኛውም ኢትዮጵያዊ’ እኔን ያቀፈ ማዕቀፍ ይሆንን?
በቀን አንዴ ትርፍራፊ ለመቅመስ መስገብገብ፣ ጎዳና ላይ በገነባቻት የላስቲክ ቤት አጠገብ ተቀምጣ የምትለምን ወፈፍ የሚያደርጋት እናት፣መለመኛ የሆኑ መንታ ታናናሽ እህትና ወንድም፣ አስር ሳንቲም ለመመፅወት የሚመፃደቅ ሂያጅ፣ በባዶ እግርና በእኮዮች ምፀት ታጅቤ የምዳክርበት ትምህርት ቤት…….. ከማንኛውም ኢትዮጵያዊ የተለየ ልጅነት ነው።
ማንኛውም ኢትዮጵያዊ እናቱ ልመናን ተናዛለት አባት አልባ ህፃናት መንገድ ዳር አስታቅፋው አልሞተችም።
ማንኛውም ኢትዮጵያዊ እናቱ የሚበር መኪና ውስጥ ገብታ ስትሞት የሚሰማውን ከእብደት ያልተለየ ስሜት አያውቀውም።
የኔ ልጅነት ‘እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ’ የሚባለው ማዕቀፍ ውስጥ የማይገባው ልጅነት የሚባለው ዘመኔ በአስር ዓመቴ አክትሞ የሁለት አመት ጨቅላ መንታ ታናናሾቼን እየለመንኩ ማሳደግ ግዴታዬ ስለነበር ነው። ዓለም ስትከረፋብኝ፣ በርሃብ ከሚጮሁ ታናናሾቼ ጋር ኡኡኡ ብዬ ሳለቅስ “እንደእናቷ ጠሸሸች” እተባልኩ አራት ዓመታትን ጎዳና መግፋቴ ነበር።
አንድ ምሽት ታናናሾቼን አስተኝቼ ነትቦ እርቃኔን ያጋለጠውን ልብሴን እየሳብኩ ከላስቲክ ጎጆአችን ፊት ለፊት ቆሚያለሁ። መኪና ሲጢጥ ብሎ ሲቆም ሰማሁ። የሰከረ ወንድ ድምፅ ተከትሎ ተሰማኝ።
“እሙዬ ነይ እስኪ……”
🌑ይቀጥላል➡️
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ የኔ ምርጦች
አመሰግናለው
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍4
#ጨረቃ_ና_ናፍቆት
#እቱ_የጥንቲቱ
የጥርስሽ ንጣቱ
የጉንጭሽ ቅላቱ
ውል ይለኛል ዛሬም የገላሽ ሙቀቱ
የእግሮችሽ ኮሽታ
የፍቅርሽ ሹክሹክታ
ያ የሣቅሽ ዜማ የበዛው ክትክታ
ይሠማኛል ዛሬም ናፍቆት ሲበረታ
#እቱ_የጥንቲቱ
አንቺም ትዝ ካለሽ ካለብሽ ናፍቆቱ
ይህ ነው መዳኒቱ
ባስለመድኩሽ ሰዓት ባለሽበት ቦታ
ቀና በይ ላንድ አፍታ
እኔም ባለሁበት ባስለመድሽኝ ሰዓት
ዓይኖቼን አቅንቼ
ጨረቃን አይቼ ልግባ ተፅናንቼ
አንቺም በዚያች አፍታ
ጨረቃዋን ፈክታ
ካየሻት ተጽናኚ
በይ ቃሌን እመኚ
ምንም ብንራራቅ ካንድ ሰማይ ሥር ነን
ነገ አብረን ለመኖር ታላቅ ተሥፋ አለን
🔘ሳምሶን መኮንን🔘
#እቱ_የጥንቲቱ
የጥርስሽ ንጣቱ
የጉንጭሽ ቅላቱ
ውል ይለኛል ዛሬም የገላሽ ሙቀቱ
የእግሮችሽ ኮሽታ
የፍቅርሽ ሹክሹክታ
ያ የሣቅሽ ዜማ የበዛው ክትክታ
ይሠማኛል ዛሬም ናፍቆት ሲበረታ
#እቱ_የጥንቲቱ
አንቺም ትዝ ካለሽ ካለብሽ ናፍቆቱ
ይህ ነው መዳኒቱ
ባስለመድኩሽ ሰዓት ባለሽበት ቦታ
ቀና በይ ላንድ አፍታ
እኔም ባለሁበት ባስለመድሽኝ ሰዓት
ዓይኖቼን አቅንቼ
ጨረቃን አይቼ ልግባ ተፅናንቼ
አንቺም በዚያች አፍታ
ጨረቃዋን ፈክታ
ካየሻት ተጽናኚ
በይ ቃሌን እመኚ
ምንም ብንራራቅ ካንድ ሰማይ ሥር ነን
ነገ አብረን ለመኖር ታላቅ ተሥፋ አለን
🔘ሳምሶን መኮንን🔘
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ_ጉዞ
:
#ክፍል_አስራ_አራት
:
✍ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
....ቀጥታ ወደቤቴ በመሄድ ፋንታ ብቻዬን ሆኜ በፀጥታ ወደምተክዝበት ቦታ ነበር የተጓዝኩት፡፡ወደቢሾፍቱ ሀይቅ ሄድኩና ቁጥቆጦ ጥቅጥቅ ካለበት ቦታ ሀይቁ ዳር ላይ ወደሚገኝ ገዘፍ ካለ የድንጋይ አለት ላይ ቁጭ ብዬ አይኖቼን አስፈሪው እና ዙሪያውን በተራራ በተከበበው ሀይቅ ላይ ተክዬ ማሰላሰል ጀመርኩ .፡፡ሙሉ አዕምሮዬን የሞላችው ዶክተሯ ነች…እኔ እንጃ አላውቅም በውስጤ ህይወቴ ሙሉ በሙሉ እንደሚቀየር እና እስከአሁን ስሄድበት ከነበረበት መንገድ ፍፅም በተቃራኒና በማይገመት አይነት መስመር መጎዝ እንደምጀምር እየተሰማኝ ነው፡፡ከሀሳቤ ሳልፈልግ ያናጠበኝ ከቆጥኞቹ ስር የሚሰማዋ መንሾካሾክ ነው፡፡ሰው መጥቶ ፀጥታዬን ሊረብሸው ነው እንዴ ? ብዬ ትኩረቴን ከሀይቁ ወደቁጥቆጦው ስመልስ ያልጠበቅኩት ነገር አየው …..ግዙፍ ዥንጉርጉር ጥቁር እባብ ሽልልል እያለ ከቋጥኙ ውስጥ ቅጠሎችንና ቅርንጫፎቹን እየገላለጠ ወደ እኔ አቅጣጫ እየተሳባ እየመጣ ነው..
ወደእኔ በመገስገስ ላይ ያለውን እባብ ምላሱን በደም ስሬ ሰክቶ መርዙን ወደውስጤ ለመትፈት የቆመጠ በሚያስመስለበት ሁኔታ ጭንቅላቱን በአየር ላይ አንሳፎ አስፈሪውን ሹል ምላሱን ትሪዕታዊ በሆነ ሁኔታ ሲያወዛውዛቸው እያየው ነው፡፡ በድንጋጤም በመገረምም ከተቀመጥኩበት ቋጥኝ በቅልጥፍና ተነሳውና ዙሪያ ገባዬኝ ማቃኘት ጀመርኩ… ጭንቅላቱን ብዬ የምገላግልበት ደህና ዱላ ነገር ፍለጋ …ያን ያህል አስተማማኝ ባይሆንም አንድ ሁለት ክንድ የሚረዝም ደረቅ እንጨት አገኘውና አፈፍ አድርጌ አነሳውና አስተካክዬ ያዝኩትና ለፍልሚያ ተዘጋጀው…….፡፡
በእኔ እና በእባቡ መካከል ያለው ክፍተት ከሁለት ሜትር አይበልጥም…እኔም እንዴት አድርጌ ላጥቃው እያልኩ እስትራቴጂ ሳወጣ 3 የሚሆኑ ደቂቃዎች አለፉ …እባቡም ከእኔ ተመሳሳዩን እያሰበ ይመስለኛል፡፡ከዛ ቀድሞ ያጠቃል ብዬ በምጠብቅበት ጊዜ በሚገርም ፍጥነት ተወርውሮ ወደመጣት ዞረና ተስፈንጥሮ ቁጥቋጦው ውስጥ ተመልሶ ገባ ፡፡ድላዬን እንደቀሰርኩ ተከተልኩት…ሊያመልጠኝ አይገባም..ደረስኩና ቁጥቋጦውን በጥንቃቄ ስገላልጥ በዛኛው ወገን ያልጠበቅኩት ነገር አያው ..ድንጋጤዬ ጨመረ.. ፈጣን ውሳኔ ወሰንኩ ..ቁጥቆጦውን በግራ በኩል አልፌ ተጠምዘዝኩና ስሮ ደረስኩና ወገቧን በአንድ እጄ አቅፌ አንጠለጠልኩና ከቁጥቆጦ ውስጥ አርቄ በመውሰድ መልሼ አስቀመጥኳት..
-ምን እያደረክ ነው?በሳቅና በመኮሳተር መሀል ባለ ስሜት ጠየቀቺኝ፡፡
-አንቺው ንገሪኝ እንጄ .እዚህ ምን እያደረግሽ ነው... ? እንዴት መጣሽ ..?.ለምን መጣሽ..?
-አንተን ለማግኘት ነዋ የመጣውት
-እኔ እዚህ እንዳሆንኩ ማን ነገረሽ… ? ውይ ይቅርታ ለካ አንቺ ነሽ››
-አዎ እኔ ነኝ…ግን ምን አየሆንክ ነው ዱላው ለማን ነው ?
-ባክሽ አንድ እባብ ሊያጠቃኝ ነበር …ግን ሀሳቡን ቀይሮ ወደእዚህ ቋጥኝ ገባብኝ … አንቺንም ሊያጠቃሽ ይችል ነበር
-እኔን እንኳን አያጠቃኝም?
-ለምን ?
-ያየኸው እባብ እራሴው ነበርኩ….እራሴን በራሴ እንዴት ላጠቃ እችላለው?፡፡
-ቀልዴን እንኳን አይደለም…ጭንቅላቱን ማለት ነበረብኝ››
-ለምን.?
-እባብ ደግሞ ለምን ይባላል ? የሰው ልጅ እና እባብ ለዘመናት ያላቸውን ጠብ እያወቅሽ… ? ለማንኛውም ነይ ብዬ ቀድሞ ወደነበርኩበት ቆጥኝ ድንጋይ ይዤት ሄድኩና ቀድሜት ተቀመጥኩ ተከተለቺኝና ከገጎኔ ተቀመጠች፡፡
-እኔ ግን ስለሰው እና እባብ ግንኙነት ተቃራኒውን ነው የማውቀው …በማለት ወደ አቋረጠነው ውይይት መለሰችን
-እንዴት ማለት እስኪ አስረጂኝ አልኳት ? ይህቺ ተምረኛ ልጅ ሳለስበው ባገኘዋት ቅፅበት የመጀመሪያ ውይይታችን ስለእባብ የመሆኑ አጋጣሚ ገርሞኝ፡፡
-እሷ ኮስተር ብላ ማብራራት ጀመረች፡፡
‹‹የእባብና የሰው ልጅ እውቅናም ሆነ ልባዊ ወዳጅነት ጥንታዊና መሰረት ያለው ነው፡፡የሰው ልጅ አግዜያብሄር በመልኩና በሀምሳሉ ፈጠረው፡፡የዘን ጊዜ ከጦጣ ወይም ከዝንጀሮ ብዙም የማይሻል ነበር፡፡አንድ ነገር በቃ ልክ እንደ እኛ እና እንደ እግዜያብሄር ከፈጣራቸው ነገሮች መካከል መናገር የሚችል ቢሆንም ከእኛ እኩል ግን የማሰብ ጥበብ አልነበረውም፡፡እግዜያብሄር እንደዛ እንዲሆን አልፈቀደም ነበር፡፡በዚህ ጊዜ የእኔ አባት ቀዳሚው እባብ በውስጥ ሀዘኔታ ገባው፡፡››
-ቆይ ነገሮችን ግልጽ እያደረግሺልኝ ሂጂ..እያወራሽ ያለሽውን እያስተዋልሽ ነው…እባብ ነኝ እያልሺኝ ነው…የሰው ስጋ ለብሼ እንደሰው ማሰብና እንደሰው መሰራት የምችል ለየት ያልኩ ፍጡር ነኝ እያልሺኝ ነው ? ››
-ለየት ያልኩ ፍጡር መሆኔን ትጠራጠራለህ እንዴ?
-አረ በፍፅም …እባብ ነኝ ያልሺውን ነው ማመን ያልቻልኩት ?
-መብተህ ነው …በሂደት ታምናለህ …እስከዛው ዝም ብለህ ተረት እያወራውህ እንደሆነ አድርገህ ስማኝ ..
-እሺ ተስማምቼያለው..ቀጥይ
- እንዳልኩህ እኛ የእባብ ዝርያዎች ቀደምት ስንፈጠር እንደሰው ልጅ በእግዜያብሄር ሀምሳል ባንፈጠርም ቆሞ በእግር መሄድ፤መናገርና ፤ክፉውንና ደጉን፤ ሚጠቅምና ሚጎዳውን በጥበብ አንጥሮ እንደእግዚያሄር ከማሰብ ፀጋ ጋር ነበር የተፈጠርነው፡፡ይሁን እንጂ እግዚያብሄር በወቅቱ በዛ ነገር ደስተኛ አልነበረም፡፡
-ምን ማለትሽ ነው…? እግዚያብሄር አይደለም የፈጠራችሁ ?››
-አዎ እራሱ ነው ? ››
-ታዲያ እሱ አስቦና ፈቅዶ ከፈጠራችሁ ብኃላ እንዴት ደስተኛ ላይሆን ይችላል ? ፡፡
-በእኛ ብቻ እኮ አይደለም ቡኃላም እናንተን ከፈጠረ ቡኃላ ተፀፅቷል ፤ለዚህ ማስረጃ ደግሞ መፃፍ ቅዱሳችሁ‹‹እግዜያብሄር ሰውን በመፍጠሩ ተፀፀተ››ይላል፡፡
-ገባኝ ተዲያ እንዴት ሆናችሁ?....ጠየቅኳት በተረቷ ተመስጬ
-የእኛ ዝርያ ባለው ጥበብ ልክ እንደ እግዚያብሄር ክፉና ደጉን አንጥሮ ማሰብንና …ያሰበወንም ማድረግ በመቻሉ በወቅቱ በነበሩት ፍጥረታት ላይ ድንጋሬ ነበረ…
-ምን አይነት ድንጋሬ?
-አምላካችን የትኛው ነው.. የሚል?
-እና እግዚያብሄርነት… በጥበብና በፍጽሞና ማሰብን ብቻ ሳይሆን ዘላለማዊነትንና ሁለንተናዊአዋቂነትን መያዝ ይጠይቃል…
በዚህ መካከል የሰው ልጅ እግዜያብሄርን መስሎ ተፈጠረ…ከዛ አባቴም በእግዜያብሄር ላይ አቂሞ ነበርና ለዚህ የስው ልጅ ለሚባል አዲስ ፍጥረት እንዴት እግዜያብሄር እንደሚሆን ላስተምረው ብሎ በቀናነት ተነሳ…
-እርግጠኛ ነሽ በቀናነት ነው ?
-እግዚያብሄር ለመሆን የሚያስፈልጉ ሁሉን አዋቂነት እና ዘላለማዊነትን የሚያስገኙ በገነት አትብሉ ብሎ ያገዳቸውን እንዲበሉ በሴቷ በኩል ምክር ለገሳቸው፡፡…የመጀማሪያዋን በልተው ሁለተኛውን ከመድገማቸው በፊት ግን ሲርበተበቱ ደረሰባቸው …
-ምን ጠቀማቸው ታዲያ ከገነት እንዲባረረ ምክንያት ነው የሆናቸው ? ፡፡..የእኔ አስተያየት ነበር፡፡
-እሱ የራሳቸው መንከርፈፍ ነው..ደግሞ እንዳለው ነው… ክፉና ደጉን ያወቁት አባቴ ብሉ ያለችውን እጽ ከበሉ ቡኃላ ነው ሁለተኛውንም ዕፅ በልተው ቢሆን ኖሮ ልክ እንደ እሱ ይሆኑ ነበር…አባራሪና ተባራሪ አይኖርም ነበር
-ያልገባኝ ነገር ታዲያ አባትሽ ማለቴ አባቡ ከዚህ ምን ይጠቀማል..እንደውም ሁለተኛ እግዚያብሄር በላዩ ላይ ይነግስ ነበር…
-አይ የአባቴ እቅድማ ሶስት እግዚያሄር እንዲኖር ነበር…
-እንዴት ሆኖ ?
-ከሄዋን ጋር ሚስጥራዊ ውለታ ነበራው፡፡አባቴ የሚፈልጋትን ሁለተኛዋን ዕጽ ለእሷ እና ለአዳም ስትቆርጥ ለእሱም ለሚስቱና ለልጁ የሚበቃ እንድታመጣለት፡፡ከዛ በሶስት ግዛቶች የተከፋፈለ ሶስት እግዜያብሄር ይኖር ነበር፡፡እቅዱ እንደዛ ነበር፡፡ከዛ ሲርበተበቱ ተያዙ እራሳቸውም
:
#ክፍል_አስራ_አራት
:
✍ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
....ቀጥታ ወደቤቴ በመሄድ ፋንታ ብቻዬን ሆኜ በፀጥታ ወደምተክዝበት ቦታ ነበር የተጓዝኩት፡፡ወደቢሾፍቱ ሀይቅ ሄድኩና ቁጥቆጦ ጥቅጥቅ ካለበት ቦታ ሀይቁ ዳር ላይ ወደሚገኝ ገዘፍ ካለ የድንጋይ አለት ላይ ቁጭ ብዬ አይኖቼን አስፈሪው እና ዙሪያውን በተራራ በተከበበው ሀይቅ ላይ ተክዬ ማሰላሰል ጀመርኩ .፡፡ሙሉ አዕምሮዬን የሞላችው ዶክተሯ ነች…እኔ እንጃ አላውቅም በውስጤ ህይወቴ ሙሉ በሙሉ እንደሚቀየር እና እስከአሁን ስሄድበት ከነበረበት መንገድ ፍፅም በተቃራኒና በማይገመት አይነት መስመር መጎዝ እንደምጀምር እየተሰማኝ ነው፡፡ከሀሳቤ ሳልፈልግ ያናጠበኝ ከቆጥኞቹ ስር የሚሰማዋ መንሾካሾክ ነው፡፡ሰው መጥቶ ፀጥታዬን ሊረብሸው ነው እንዴ ? ብዬ ትኩረቴን ከሀይቁ ወደቁጥቆጦው ስመልስ ያልጠበቅኩት ነገር አየው …..ግዙፍ ዥንጉርጉር ጥቁር እባብ ሽልልል እያለ ከቋጥኙ ውስጥ ቅጠሎችንና ቅርንጫፎቹን እየገላለጠ ወደ እኔ አቅጣጫ እየተሳባ እየመጣ ነው..
ወደእኔ በመገስገስ ላይ ያለውን እባብ ምላሱን በደም ስሬ ሰክቶ መርዙን ወደውስጤ ለመትፈት የቆመጠ በሚያስመስለበት ሁኔታ ጭንቅላቱን በአየር ላይ አንሳፎ አስፈሪውን ሹል ምላሱን ትሪዕታዊ በሆነ ሁኔታ ሲያወዛውዛቸው እያየው ነው፡፡ በድንጋጤም በመገረምም ከተቀመጥኩበት ቋጥኝ በቅልጥፍና ተነሳውና ዙሪያ ገባዬኝ ማቃኘት ጀመርኩ… ጭንቅላቱን ብዬ የምገላግልበት ደህና ዱላ ነገር ፍለጋ …ያን ያህል አስተማማኝ ባይሆንም አንድ ሁለት ክንድ የሚረዝም ደረቅ እንጨት አገኘውና አፈፍ አድርጌ አነሳውና አስተካክዬ ያዝኩትና ለፍልሚያ ተዘጋጀው…….፡፡
በእኔ እና በእባቡ መካከል ያለው ክፍተት ከሁለት ሜትር አይበልጥም…እኔም እንዴት አድርጌ ላጥቃው እያልኩ እስትራቴጂ ሳወጣ 3 የሚሆኑ ደቂቃዎች አለፉ …እባቡም ከእኔ ተመሳሳዩን እያሰበ ይመስለኛል፡፡ከዛ ቀድሞ ያጠቃል ብዬ በምጠብቅበት ጊዜ በሚገርም ፍጥነት ተወርውሮ ወደመጣት ዞረና ተስፈንጥሮ ቁጥቋጦው ውስጥ ተመልሶ ገባ ፡፡ድላዬን እንደቀሰርኩ ተከተልኩት…ሊያመልጠኝ አይገባም..ደረስኩና ቁጥቋጦውን በጥንቃቄ ስገላልጥ በዛኛው ወገን ያልጠበቅኩት ነገር አያው ..ድንጋጤዬ ጨመረ.. ፈጣን ውሳኔ ወሰንኩ ..ቁጥቆጦውን በግራ በኩል አልፌ ተጠምዘዝኩና ስሮ ደረስኩና ወገቧን በአንድ እጄ አቅፌ አንጠለጠልኩና ከቁጥቆጦ ውስጥ አርቄ በመውሰድ መልሼ አስቀመጥኳት..
-ምን እያደረክ ነው?በሳቅና በመኮሳተር መሀል ባለ ስሜት ጠየቀቺኝ፡፡
-አንቺው ንገሪኝ እንጄ .እዚህ ምን እያደረግሽ ነው... ? እንዴት መጣሽ ..?.ለምን መጣሽ..?
-አንተን ለማግኘት ነዋ የመጣውት
-እኔ እዚህ እንዳሆንኩ ማን ነገረሽ… ? ውይ ይቅርታ ለካ አንቺ ነሽ››
-አዎ እኔ ነኝ…ግን ምን አየሆንክ ነው ዱላው ለማን ነው ?
-ባክሽ አንድ እባብ ሊያጠቃኝ ነበር …ግን ሀሳቡን ቀይሮ ወደእዚህ ቋጥኝ ገባብኝ … አንቺንም ሊያጠቃሽ ይችል ነበር
-እኔን እንኳን አያጠቃኝም?
-ለምን ?
-ያየኸው እባብ እራሴው ነበርኩ….እራሴን በራሴ እንዴት ላጠቃ እችላለው?፡፡
-ቀልዴን እንኳን አይደለም…ጭንቅላቱን ማለት ነበረብኝ››
-ለምን.?
-እባብ ደግሞ ለምን ይባላል ? የሰው ልጅ እና እባብ ለዘመናት ያላቸውን ጠብ እያወቅሽ… ? ለማንኛውም ነይ ብዬ ቀድሞ ወደነበርኩበት ቆጥኝ ድንጋይ ይዤት ሄድኩና ቀድሜት ተቀመጥኩ ተከተለቺኝና ከገጎኔ ተቀመጠች፡፡
-እኔ ግን ስለሰው እና እባብ ግንኙነት ተቃራኒውን ነው የማውቀው …በማለት ወደ አቋረጠነው ውይይት መለሰችን
-እንዴት ማለት እስኪ አስረጂኝ አልኳት ? ይህቺ ተምረኛ ልጅ ሳለስበው ባገኘዋት ቅፅበት የመጀመሪያ ውይይታችን ስለእባብ የመሆኑ አጋጣሚ ገርሞኝ፡፡
-እሷ ኮስተር ብላ ማብራራት ጀመረች፡፡
‹‹የእባብና የሰው ልጅ እውቅናም ሆነ ልባዊ ወዳጅነት ጥንታዊና መሰረት ያለው ነው፡፡የሰው ልጅ አግዜያብሄር በመልኩና በሀምሳሉ ፈጠረው፡፡የዘን ጊዜ ከጦጣ ወይም ከዝንጀሮ ብዙም የማይሻል ነበር፡፡አንድ ነገር በቃ ልክ እንደ እኛ እና እንደ እግዜያብሄር ከፈጣራቸው ነገሮች መካከል መናገር የሚችል ቢሆንም ከእኛ እኩል ግን የማሰብ ጥበብ አልነበረውም፡፡እግዜያብሄር እንደዛ እንዲሆን አልፈቀደም ነበር፡፡በዚህ ጊዜ የእኔ አባት ቀዳሚው እባብ በውስጥ ሀዘኔታ ገባው፡፡››
-ቆይ ነገሮችን ግልጽ እያደረግሺልኝ ሂጂ..እያወራሽ ያለሽውን እያስተዋልሽ ነው…እባብ ነኝ እያልሺኝ ነው…የሰው ስጋ ለብሼ እንደሰው ማሰብና እንደሰው መሰራት የምችል ለየት ያልኩ ፍጡር ነኝ እያልሺኝ ነው ? ››
-ለየት ያልኩ ፍጡር መሆኔን ትጠራጠራለህ እንዴ?
-አረ በፍፅም …እባብ ነኝ ያልሺውን ነው ማመን ያልቻልኩት ?
-መብተህ ነው …በሂደት ታምናለህ …እስከዛው ዝም ብለህ ተረት እያወራውህ እንደሆነ አድርገህ ስማኝ ..
-እሺ ተስማምቼያለው..ቀጥይ
- እንዳልኩህ እኛ የእባብ ዝርያዎች ቀደምት ስንፈጠር እንደሰው ልጅ በእግዜያብሄር ሀምሳል ባንፈጠርም ቆሞ በእግር መሄድ፤መናገርና ፤ክፉውንና ደጉን፤ ሚጠቅምና ሚጎዳውን በጥበብ አንጥሮ እንደእግዚያሄር ከማሰብ ፀጋ ጋር ነበር የተፈጠርነው፡፡ይሁን እንጂ እግዚያብሄር በወቅቱ በዛ ነገር ደስተኛ አልነበረም፡፡
-ምን ማለትሽ ነው…? እግዚያብሄር አይደለም የፈጠራችሁ ?››
-አዎ እራሱ ነው ? ››
-ታዲያ እሱ አስቦና ፈቅዶ ከፈጠራችሁ ብኃላ እንዴት ደስተኛ ላይሆን ይችላል ? ፡፡
-በእኛ ብቻ እኮ አይደለም ቡኃላም እናንተን ከፈጠረ ቡኃላ ተፀፅቷል ፤ለዚህ ማስረጃ ደግሞ መፃፍ ቅዱሳችሁ‹‹እግዜያብሄር ሰውን በመፍጠሩ ተፀፀተ››ይላል፡፡
-ገባኝ ተዲያ እንዴት ሆናችሁ?....ጠየቅኳት በተረቷ ተመስጬ
-የእኛ ዝርያ ባለው ጥበብ ልክ እንደ እግዚያብሄር ክፉና ደጉን አንጥሮ ማሰብንና …ያሰበወንም ማድረግ በመቻሉ በወቅቱ በነበሩት ፍጥረታት ላይ ድንጋሬ ነበረ…
-ምን አይነት ድንጋሬ?
-አምላካችን የትኛው ነው.. የሚል?
-እና እግዚያብሄርነት… በጥበብና በፍጽሞና ማሰብን ብቻ ሳይሆን ዘላለማዊነትንና ሁለንተናዊአዋቂነትን መያዝ ይጠይቃል…
በዚህ መካከል የሰው ልጅ እግዜያብሄርን መስሎ ተፈጠረ…ከዛ አባቴም በእግዜያብሄር ላይ አቂሞ ነበርና ለዚህ የስው ልጅ ለሚባል አዲስ ፍጥረት እንዴት እግዜያብሄር እንደሚሆን ላስተምረው ብሎ በቀናነት ተነሳ…
-እርግጠኛ ነሽ በቀናነት ነው ?
-እግዚያብሄር ለመሆን የሚያስፈልጉ ሁሉን አዋቂነት እና ዘላለማዊነትን የሚያስገኙ በገነት አትብሉ ብሎ ያገዳቸውን እንዲበሉ በሴቷ በኩል ምክር ለገሳቸው፡፡…የመጀማሪያዋን በልተው ሁለተኛውን ከመድገማቸው በፊት ግን ሲርበተበቱ ደረሰባቸው …
-ምን ጠቀማቸው ታዲያ ከገነት እንዲባረረ ምክንያት ነው የሆናቸው ? ፡፡..የእኔ አስተያየት ነበር፡፡
-እሱ የራሳቸው መንከርፈፍ ነው..ደግሞ እንዳለው ነው… ክፉና ደጉን ያወቁት አባቴ ብሉ ያለችውን እጽ ከበሉ ቡኃላ ነው ሁለተኛውንም ዕፅ በልተው ቢሆን ኖሮ ልክ እንደ እሱ ይሆኑ ነበር…አባራሪና ተባራሪ አይኖርም ነበር
-ያልገባኝ ነገር ታዲያ አባትሽ ማለቴ አባቡ ከዚህ ምን ይጠቀማል..እንደውም ሁለተኛ እግዚያብሄር በላዩ ላይ ይነግስ ነበር…
-አይ የአባቴ እቅድማ ሶስት እግዚያሄር እንዲኖር ነበር…
-እንዴት ሆኖ ?
-ከሄዋን ጋር ሚስጥራዊ ውለታ ነበራው፡፡አባቴ የሚፈልጋትን ሁለተኛዋን ዕጽ ለእሷ እና ለአዳም ስትቆርጥ ለእሱም ለሚስቱና ለልጁ የሚበቃ እንድታመጣለት፡፡ከዛ በሶስት ግዛቶች የተከፋፈለ ሶስት እግዜያብሄር ይኖር ነበር፡፡እቅዱ እንደዛ ነበር፡፡ከዛ ሲርበተበቱ ተያዙ እራሳቸውም
👍4👎2❤1
ከገነት ተባረው እኛን እንድንባረር አደረጉን፡፡በተለይ እኛ በጣም ነው የተጎዳነው፡፡
-እስቲ ስለዕወቀት ፍሬዋ ንገሪኝ ?
-ስለእሷ ምን ልንገርህ?
-የዛን ጊዜ አንደበሉ በአዳምና ሄዋን ላይ ያስከተለው ለውጥ፡
-ፍሬዋ እንደምታስባት በአንዴ ሁሉን ነገር ግልጽ ምታደርግ አይደለችም….ቁልፍ በላት ፡፡የሆነ መግባት የምትፈልግበት ቤት ቁልፍ ስታገኝ ሰረገላ ውስጥ መክፈቻውን ትከተዋለህ ከዛ ታሽከረክረዋለህ…ትከፍተውና ወደ ውስጥ በመግባት የምትፍልገውን ነገር ለማግኘት መዞዞርና በየክፍሉ መቃኘት አለብህ፡፡
-ያቺ ዕፅ ማለት ቁልፍ ብቻ ነች፡፡ሰውን ማሰብ እንዲችል ወይም ክፉና ደጉን መለየት እንዲችል መጋረጃውን መክፈቻ..ለሌው ግን በአንዴ የሚሆን አይደለም፡፡ፍሬው ልክ እንደወይን በአመታተ ቆይታ ኃይል እየጨመረ እና ጣዕሙ እያማራ ሚሄድ ነው፡፡ከአባት ወደልጅ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲሸጋገር ይበልጥ እየጠለቀ እና እያደገ የሚሄድ እውቀትና መገለፅ ከአባት ወደልጅ ፤ከዛም ወደልጅ ልጅ እየተሸጋገረ በሄደ ቁጥር እየዳበረ እና በዕወቀት እየበለፀገ የሚሄድ ነው፡፡
-ቆይ እሺ እሱን ለጊዜው ተይውና እናቴን ስላዳንሺልኝ እንዴት እንደማመሰግንሽ አላውቅም፡፡
-እንድታመሰግነኝ አይደለም ያደረኩልህ …በመልሱ እንድታገባኝ ስለምፈልግ ነው፡፡
-የእወነቴን ነው አትቀልጂ…በጣም ነው የማመሰግንሽ›
-እኔም የእወነቴን ነው…ካንተ ሁለት ነገር ነው የምፈልገው …አንድ እንድንጋባ እና አንድ ልጅ እንድንወልድ …ሁለተኛውን ደግሞ ሌላ ቀን ነገርሀለው…አለቺኝ ኮስተር ብላ
-እኔም ይህቺ ገራሚ ሴት እውነተዋን ይሆን እንዴ ? ስል ሌላ የሀሳብ መብሰልሰል ውስጥ ገባው።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
-እስቲ ስለዕወቀት ፍሬዋ ንገሪኝ ?
-ስለእሷ ምን ልንገርህ?
-የዛን ጊዜ አንደበሉ በአዳምና ሄዋን ላይ ያስከተለው ለውጥ፡
-ፍሬዋ እንደምታስባት በአንዴ ሁሉን ነገር ግልጽ ምታደርግ አይደለችም….ቁልፍ በላት ፡፡የሆነ መግባት የምትፈልግበት ቤት ቁልፍ ስታገኝ ሰረገላ ውስጥ መክፈቻውን ትከተዋለህ ከዛ ታሽከረክረዋለህ…ትከፍተውና ወደ ውስጥ በመግባት የምትፍልገውን ነገር ለማግኘት መዞዞርና በየክፍሉ መቃኘት አለብህ፡፡
-ያቺ ዕፅ ማለት ቁልፍ ብቻ ነች፡፡ሰውን ማሰብ እንዲችል ወይም ክፉና ደጉን መለየት እንዲችል መጋረጃውን መክፈቻ..ለሌው ግን በአንዴ የሚሆን አይደለም፡፡ፍሬው ልክ እንደወይን በአመታተ ቆይታ ኃይል እየጨመረ እና ጣዕሙ እያማራ ሚሄድ ነው፡፡ከአባት ወደልጅ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲሸጋገር ይበልጥ እየጠለቀ እና እያደገ የሚሄድ እውቀትና መገለፅ ከአባት ወደልጅ ፤ከዛም ወደልጅ ልጅ እየተሸጋገረ በሄደ ቁጥር እየዳበረ እና በዕወቀት እየበለፀገ የሚሄድ ነው፡፡
-ቆይ እሺ እሱን ለጊዜው ተይውና እናቴን ስላዳንሺልኝ እንዴት እንደማመሰግንሽ አላውቅም፡፡
-እንድታመሰግነኝ አይደለም ያደረኩልህ …በመልሱ እንድታገባኝ ስለምፈልግ ነው፡፡
-የእወነቴን ነው አትቀልጂ…በጣም ነው የማመሰግንሽ›
-እኔም የእወነቴን ነው…ካንተ ሁለት ነገር ነው የምፈልገው …አንድ እንድንጋባ እና አንድ ልጅ እንድንወልድ …ሁለተኛውን ደግሞ ሌላ ቀን ነገርሀለው…አለቺኝ ኮስተር ብላ
-እኔም ይህቺ ገራሚ ሴት እውነተዋን ይሆን እንዴ ? ስል ሌላ የሀሳብ መብሰልሰል ውስጥ ገባው።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍2
#ሽ_ወይም_ሺ_ጨምሪበት
ታምሜ ከአልጋ ፥ ተሰፍቼ ስውል
መላ አካላቴ ፥ ቅንጥስ ስብር ሲል
ህመሜን ረስቼ ፥ ጤናሽ ያሳሰበኝ
በሽታ ሳይነካሽ ፥ ጤናሽ ያስጨነቀኝ
'ወድጄ' አይምሰልሽ ፥ እንዲያ ምንከራተት
ይልቁስ ከገባሽ ፥ 'ሽ' ጨምሪበት
ስላንቺ ማሰቤን ፥ ከልቤ አምርሬ
መወድዴን ስነግርሽ ፥ አንቺኑ ማፍቀሬ
ከቁብም ሳትቀጥሪው ፥ የያዘኝን ፍቅር
እንዳልሰማ ሆነሽ ፥ ስትይብኝ ዞር
እኔም ሳይሰለቸኝ ፥ ደግሜ ስነግርሽ
በመሰላቸት 'እ' ፥ ነበረ መልስሽ
ጭራሽ ሳልሰላች ፥ ከቶውን ሳልታክት
እኔ እልሻለሁ ፥ 'ሺ' ጨምሪበት
ማነው እሱ ካሉሽ፥ ካሻሽ ንገሪያቸው
ህመምሽ የሚያመው ፥ ጤናሽ ሚያሳስበው
መውደዱን ሲነግርሽ ፥ ግራ ቀኝ ያጋባሽ
ገገማ የሆነ ፥ ያሰለቸሽ ጭራሽ
ኧረ ማነው እሱ ፥ ብለው ከጠየቁሽ
'ሺበ' ሚለው ቃል ላይ ፥ ሺ ጨምሪበት
እናልሽ
ሕመሜን ዘንግቼ የቆየሁ ወድጄ-ሽ
መውደዴን ስነግርሽ እ-ሺ በይም ያልኩሽ
ሺበ-ሺ እባላለሁ እኔ፥ ምስኪኑ አፍቃሪሽ
ከአትሮኖስ ቻናል ተከታታይ የተላከ
👉 @cleopas4 አስተያየታችሁን አድርሱት
ታምሜ ከአልጋ ፥ ተሰፍቼ ስውል
መላ አካላቴ ፥ ቅንጥስ ስብር ሲል
ህመሜን ረስቼ ፥ ጤናሽ ያሳሰበኝ
በሽታ ሳይነካሽ ፥ ጤናሽ ያስጨነቀኝ
'ወድጄ' አይምሰልሽ ፥ እንዲያ ምንከራተት
ይልቁስ ከገባሽ ፥ 'ሽ' ጨምሪበት
ስላንቺ ማሰቤን ፥ ከልቤ አምርሬ
መወድዴን ስነግርሽ ፥ አንቺኑ ማፍቀሬ
ከቁብም ሳትቀጥሪው ፥ የያዘኝን ፍቅር
እንዳልሰማ ሆነሽ ፥ ስትይብኝ ዞር
እኔም ሳይሰለቸኝ ፥ ደግሜ ስነግርሽ
በመሰላቸት 'እ' ፥ ነበረ መልስሽ
ጭራሽ ሳልሰላች ፥ ከቶውን ሳልታክት
እኔ እልሻለሁ ፥ 'ሺ' ጨምሪበት
ማነው እሱ ካሉሽ፥ ካሻሽ ንገሪያቸው
ህመምሽ የሚያመው ፥ ጤናሽ ሚያሳስበው
መውደዱን ሲነግርሽ ፥ ግራ ቀኝ ያጋባሽ
ገገማ የሆነ ፥ ያሰለቸሽ ጭራሽ
ኧረ ማነው እሱ ፥ ብለው ከጠየቁሽ
'ሺበ' ሚለው ቃል ላይ ፥ ሺ ጨምሪበት
እናልሽ
ሕመሜን ዘንግቼ የቆየሁ ወድጄ-ሽ
መውደዴን ስነግርሽ እ-ሺ በይም ያልኩሽ
ሺበ-ሺ እባላለሁ እኔ፥ ምስኪኑ አፍቃሪሽ
ከአትሮኖስ ቻናል ተከታታይ የተላከ
👉 @cleopas4 አስተያየታችሁን አድርሱት
#ቂም_የሸፈነው_እውነት
:
#ክፍል_ሁለት (የመጨረሻ ክፍል)
፧
✍ደራሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
......“ምን ፈለግክ?”
“አንቺን”
“ሸርሙጣ አይደለሁም።”
“ታዲያ እዚህ ምን ይገትርሻል?”
“ቤቴ ነዋ…..” ብዬ የላስቲክ ቤቴን በእጄ ጠቆምኩት።
“ስንት ዓመትሽ ነው?”
“አስራ አራት” ከመኪናው ወርዶ እየተንገዳገደ ተጠጋኝ።
“300 ብር እሰጥሻለሁ።”
“ሸርሙጣ አይደለሁም አልኩህ እኮ……”
“ሸርሙጣ ነሽ ማን አለሽ? ጎዳና እያደርሽ ምንም አልቀመስኩም ለማለት ነው?” እዚያ ጎዳና ላይ ስኖር ከዛ በላይ ፀያፍ ቃላቶች ሰምቼ አውቃለሁ። የዛን እለት ግን ሰውየው የተናገረው ንግግር ሰቀጠጠኝ። አጠገቤ ያገኘሁትን ድንጋይ አንስቼ ከፍ አደረግኩ
“በዚህ አናትህን ሳልከፍልህ ሂድ ከዚህ ጥፋ”
“ምንም የማታውቂ ከሆነ 1000 ብር እሰጥሻለሁ”
ደጋግሜ የብሩን መጠን ለራሴ አነበነብኩት። በህልሜ እንኳን አስቤው የማላውቅ ዓይነት ነበር። ምን ያህል ፍርሃት ቢያርደኝም ከብሩ መጠን ጋር ሲወዳደር ቀለለኝ። በዛው ቅፅበት ምን እንደማደርግ እቅድ አወጣሁ። ጭንቅላቴ እጄን አላዘዘውም። የመኪናውን በር ከፍቼ ገባሁ። ሲኦልን የዛን ምሽት አየኋት። በአለም ላይ ካሉ አስቀያሚ እና ጨካኝ ፍጥረታት መሃከል ዋነኞቹ ወንዶች መሆናቸውም የዛን እለት ገባኝ። ገና የ14 ዓመት ልጅ ነበርኩ፣ በችግር ሰውነቴ ደቆ የእድሜዬን ያህል ያላደግኩ፣ ምንም የማላውቅ………… ሰው እንዴት በህፃን ህመም ይደሰታል? እየተሰቃየሁ በፈሰሰኝ ደም እንዴት ድል እንዳደረገ ይፈነጫል? እሱ ወዙን ሲያዘንብ እኔ እንባዬ ሲዘንብ እንዴት ሰብዓዊነት አይሰማውም? እንዴት በ1000 ብሩ ስቃዬን ይገዛል? እንዴትስ ያ ደስተኛ ያደርገዋል? ይኼ ፍጡር ወንድ ነው።…… በስቃይና በተስፋ ተሰቅዤ ሊነጋ አካባቢ ወደ ላስቲክ ቤቴ ተመለስኩ። እነ አቢን ቀሰቀስኳቸው። …………… ርሃብ የለም። ልመናም የለም። ገበያ ይዣቸው ወጣሁ። ለብሰውት የማያውቁትን ልብስ ገዛሁላቸው። ካፌ ወስጄ ኬክ አበላኋቸው ጠግበን ዋልን።
በዚያው ሰሞን በተረፈኝ ገንዘብ መንገድ ላይ ሲቆሙ የማያቸው ሴቶች የሚለብሷቸውን የመሳሰሉ አልባሳት ገዛሁ። ያደርጉታል ብዬ ያሰብኩትን አደረግኩ።ይመስላሉ ብዬ ያሰብኩትን መሰልኩ። ዘወትር ማታ ሲዖል ደርሶ መልስ የኑሮዬ አንድ ክፍል ሆነ። ገንዘብ እየተቀበልኩ ስቃዬን መጨጥ (ለወንዶቹ እርካታቸውን) የየቀን ስራዬ ሆነ። አሁን ገንዘብ ማግኘት ቻልኩ። እንዳቅማችን ቤት ተከራየን እህትና ወንድሜ ትምህርት ቤት ገቡ።
ወንዶችን አልወድም ገንዘባቸውን እንጂ። ከወንድነታቸው የሚተርፈኝ ስቃይና ላባቸው ነው። ገንዘባቸው ግን የማልፈውን ሲኦል ያስረሳኛል። መንገድ መቆሙን ትቼ ትልልቅ ሆቴል ውስጥ መስራት ጀመርኩ። እንደዋዛ ትልቅ ሴት ሆንኩ። ሃያ አንድ ዓመት ሞላኝ በዚህ ወቅት ነው ካሳሁንን ያገኘሁት የሆቴሉ ደንበኛ ነው።
“ቆንጆ እኮ ነሽ እዚህ ቦታ መገኘት አልነበረብሽም::” አለኝ።
“አየህ ተፈጥሮ ቁንጅናን እንጂ የተደላደለ ህይወትን አብራ አልሰጠችኝም::” መለስኩለት።
“የዛሬ ገቢሽን ልስጥሽና እቤትሽ አርፈሽ ተኚ?”
“ይበዛብሃል::”
“እጥፍ ላድርግልሽ!!”
በራሱ መኪና እቤቴ አደረሰኝ።የጠየቅኩትን ገንዘብ ሳያቅማማ ሰጠኝ። በተደጋጋሚ እንዲህ አደረገ። ለዘመናት የሆቴሉ ደንበኛ ሲሆን ከሆቴሉ ሴቶች ጋር ስሙ ተነስቶ እንደማያውቅ ሰማሁ። ከአመታት በፊት ብቸኛ ወንድሙ ከእርሱ ጋር ተጣልቶ በባህር አቋርጦ ወደውጪ ሀገር ሊሄድ ሲሞክር የመሞቱን መርዶ ከሰማ ጀምሮ በየምሽቱ ይመጣል፣ እራቱን ይበላል፣ ይጠጣል፣ ለሴቶቹ ይጋብዛቸዋል፣… … ወደቤቱ ይሄዳል። ከቀናት በኋላ አብሬው እንዳድር በትህትና ጠየቀኝ። እቤቱ ነበር ይዞኝ የሄደው። ከሱ ጋር ካደርኩ በኋላ ወደ ሆቴል ተመልሼ መሄድ አላስፈለገኝም። በየእለቱ ማታ እቤቱ እጠብቀዋለሁ። ሲነጋ ወደቤቴ እመለሳለሁ።
እንዳገባው የጠየቀኝ ቀን እብደት የቀላቀለው ስሜት ነበር የተሰማኝ። ምክንያቱ ባል ማግኘቴ አይደለም። ባል ወንድ ነው ወንድ ደግሞ የገንዘብ ምንጭ ነው። ከዛ ያለፈ አይደለም ለኔ። ካሳሁን ብዙዎች የሚያውቁት ሀብታም ነጋዴ ነው። …… በቃ!! ብር አገኛለሁ። የትኛውም ወንድ እንደሸቀጥ የሚገዛት ሴት መሆኔ ይቀራል፣ እነ አቢዬ ያለስጋት ትምህርታቸውን ይማራሉ፣ በለውጥ ገላዬን እሰጠዋለሁ። ልቤ ያውቀዋል እንደምፈታው። ተጋባን። እህትና ወንድሜን ይዤ እኔ ገንዘብን እሱ ትዳሩን ስንጠብቅ ኖርን።
*
ሳምንታት አለፉ። ሲመቸው ለቤቱ ፕሮሰስ እንደሚመጣ ቢነግረኝም ካሳሁን አልመጣም ። አልደወለም። በቤቱ ምክንያት ቢመጣና ባየው ተመኘሁ።ቤቱ አስክሬን የወጣበት ቤት መስሎ ረጭ አለ።
የቤቱ ድምቀት፡- ትልቅነቱ፣ የቀለማቱ ስብጥር፣ በውስጡ ያጨቀው ውድ እቃ አልነበረም። ሞገሱን ተገፏል። ካሳሁን የለበትም።
የምግቡ ጣዕም የሰራተኛዋ ጥበብ አልነበረም። ከካሳሁን ጋር የምግብ ጠረጴዛው ላይ መታደሙ እንጂ።
የእንቅልፉ መጣፈጥ የአልጋው ምቾት አልነበረም በካሳሁን እቅፍ ውስጥ ማደሩ እንጂ።
ይሄ ሁሉ የገባኝ አምስት ዓመታት ዘግይቶ ሆነ። የህይወት ዘመን ልምዴንና እውቀቴን ያስከነዳው እውነት ካሳሁን ‘ሴት ልጅ ለገንዘብህ ስትል ትወድሃለች’ ብለው እንደሚያስቡ ወንዶች አልነበረም። ገንዘቡን እንደወደድኩት እንጂ ለእሱ ግድ እንደሌለኝ ያውቃል። ራሱን እንድወደው ነበር አምስት ዓመት ሙሉ ሲጥር የነበረው። የፈለግኩትን ሁሉ እንኳን አጊንቼ እሱ ከሌለበት ባዶ መሆኑን ነበር ያሳየኝ። እድሜውን ካፈራው ንብረት እንደበለጥኩበት አሳይቶኝ እድሜዬን ሙሉ የጓጓሁለት ሀብታምነት ከንቱ መሆኑን ነገረኝ። አብሬው ስኖር ያላየሁት እውነት ያ ነበር።
“ ማንም የኔን ያህል አውቆሽ አያውቅም።” ይለኝ ነበር ሁሌም ሳበሳጨው። አሁን ነው ምን ያህል እንደሚያውቀኝ የገባኝ። ባዶነቴ በፍቅር እንጂ በገንዘብ እንደማይሞላ ያውቅ ነበር። እሱ ብቻ ይሄን ያውቅ ነበር።
ስልኬን አንስቼ ደወልኩለት።
“ሰብሊ ይቅርታ ደንበኞች እያናገርኩ ነው። ቆይቼ እደውላለሁ።” ብሎኝ ስልኩን ዘጋው። ‘ቆይቼ’ ያለው ሰዓት ዘላለም መሰለኝ። ሲሊፐር እንዳጠለቅኩ ተነስቼ ከቤት ወጣሁ። እንዲህ ላብድ የሚመስለኝ ሰዓት እብደቴን የማስታግሰው እህትና ወንድሜ ጋር ስሆን ነበር። አሁን እነሱ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች ናቸው። እንድረብሻቸው አልፈልገኩም። ደግሞም ካሳሁንን የአባታቸው ያህል ነው የሚወዱት። በቀስታ እየተራመድኩ ማሰብ ጀመርኩ። አሁን ያለኝን ሁሉ አጥቼ ካሳሁንን ብቻ ማግኘት ተመኘሁ። እግሬን ጭንቅላቴ አላዘዘውም። ወደካሳሁን ቢሮ ሮጥኩ። ርቀቱ፣ አለባበሴ፣ የፀጉሬ መንጨፍረር…….. ምኑም ግድ አልሰጠኝም። ትንፍሼ ቁርጥ ቁርጥ እያለ በሩን ከፍቼ ገባሁ። ሁኔታዬ ያስደነገጣት ፀሃፊው መውጣቱን ነገረችኝ። በደከመ ነፍሴ ወደቤቴ ማዝገም ጀመርኩ። የመጣሁት መንገድ ርቀቱ የታወቀኝ ስመለስ ነው። ብዙ መንገድ ሮጫለሁ። መንገዱ ዳር ድንጋይ ላይ ተቀመጥኩ። ለብዙ ቀናት የረባ ምግብ ያለመብላቴን፣ እረፍት ያለው እንቅልፍ ያለመተኛቴን አሁን ነው ያስታወስኩት። ላዳ ይዤ ወደቤቴ ሄድኩኝ። በሩ ላይ የካሳሁንን መኪና ቆሞ ሳየው ‘እሪሪሪሪረ……’ ማለት አማረኝ። በሩጋ ስደርስ እሱ እየወጣ ነበር። ከላይ እስከታች እያስተዋለኝ
“ስደውልልሽ አታነሺም?”
“ስልኬን ጥዬው ነው የወጣሁት። ቢሮህ እኮ ሄጄ…..”
“አሁን መጥታ ነበር ሲሉኝ ነው ወደቤት የመጣሁት። ሰላም አይደለሽም?” ይዞኝ የመጣው ታክሲ ጥሩንባውን አስጮኸው።
“አልከፈልሽውም እንዴ?” ብሎ እጁን ኪሱ ውስጥ እየከተተ ወደታክሲው አመራ። በዛው የማይመለስ መሰለኝ። ድጋሚ ለሳምንታት የማላየው መሰለኝ
:
#ክፍል_ሁለት (የመጨረሻ ክፍል)
፧
✍ደራሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
......“ምን ፈለግክ?”
“አንቺን”
“ሸርሙጣ አይደለሁም።”
“ታዲያ እዚህ ምን ይገትርሻል?”
“ቤቴ ነዋ…..” ብዬ የላስቲክ ቤቴን በእጄ ጠቆምኩት።
“ስንት ዓመትሽ ነው?”
“አስራ አራት” ከመኪናው ወርዶ እየተንገዳገደ ተጠጋኝ።
“300 ብር እሰጥሻለሁ።”
“ሸርሙጣ አይደለሁም አልኩህ እኮ……”
“ሸርሙጣ ነሽ ማን አለሽ? ጎዳና እያደርሽ ምንም አልቀመስኩም ለማለት ነው?” እዚያ ጎዳና ላይ ስኖር ከዛ በላይ ፀያፍ ቃላቶች ሰምቼ አውቃለሁ። የዛን እለት ግን ሰውየው የተናገረው ንግግር ሰቀጠጠኝ። አጠገቤ ያገኘሁትን ድንጋይ አንስቼ ከፍ አደረግኩ
“በዚህ አናትህን ሳልከፍልህ ሂድ ከዚህ ጥፋ”
“ምንም የማታውቂ ከሆነ 1000 ብር እሰጥሻለሁ”
ደጋግሜ የብሩን መጠን ለራሴ አነበነብኩት። በህልሜ እንኳን አስቤው የማላውቅ ዓይነት ነበር። ምን ያህል ፍርሃት ቢያርደኝም ከብሩ መጠን ጋር ሲወዳደር ቀለለኝ። በዛው ቅፅበት ምን እንደማደርግ እቅድ አወጣሁ። ጭንቅላቴ እጄን አላዘዘውም። የመኪናውን በር ከፍቼ ገባሁ። ሲኦልን የዛን ምሽት አየኋት። በአለም ላይ ካሉ አስቀያሚ እና ጨካኝ ፍጥረታት መሃከል ዋነኞቹ ወንዶች መሆናቸውም የዛን እለት ገባኝ። ገና የ14 ዓመት ልጅ ነበርኩ፣ በችግር ሰውነቴ ደቆ የእድሜዬን ያህል ያላደግኩ፣ ምንም የማላውቅ………… ሰው እንዴት በህፃን ህመም ይደሰታል? እየተሰቃየሁ በፈሰሰኝ ደም እንዴት ድል እንዳደረገ ይፈነጫል? እሱ ወዙን ሲያዘንብ እኔ እንባዬ ሲዘንብ እንዴት ሰብዓዊነት አይሰማውም? እንዴት በ1000 ብሩ ስቃዬን ይገዛል? እንዴትስ ያ ደስተኛ ያደርገዋል? ይኼ ፍጡር ወንድ ነው።…… በስቃይና በተስፋ ተሰቅዤ ሊነጋ አካባቢ ወደ ላስቲክ ቤቴ ተመለስኩ። እነ አቢን ቀሰቀስኳቸው። …………… ርሃብ የለም። ልመናም የለም። ገበያ ይዣቸው ወጣሁ። ለብሰውት የማያውቁትን ልብስ ገዛሁላቸው። ካፌ ወስጄ ኬክ አበላኋቸው ጠግበን ዋልን።
በዚያው ሰሞን በተረፈኝ ገንዘብ መንገድ ላይ ሲቆሙ የማያቸው ሴቶች የሚለብሷቸውን የመሳሰሉ አልባሳት ገዛሁ። ያደርጉታል ብዬ ያሰብኩትን አደረግኩ።ይመስላሉ ብዬ ያሰብኩትን መሰልኩ። ዘወትር ማታ ሲዖል ደርሶ መልስ የኑሮዬ አንድ ክፍል ሆነ። ገንዘብ እየተቀበልኩ ስቃዬን መጨጥ (ለወንዶቹ እርካታቸውን) የየቀን ስራዬ ሆነ። አሁን ገንዘብ ማግኘት ቻልኩ። እንዳቅማችን ቤት ተከራየን እህትና ወንድሜ ትምህርት ቤት ገቡ።
ወንዶችን አልወድም ገንዘባቸውን እንጂ። ከወንድነታቸው የሚተርፈኝ ስቃይና ላባቸው ነው። ገንዘባቸው ግን የማልፈውን ሲኦል ያስረሳኛል። መንገድ መቆሙን ትቼ ትልልቅ ሆቴል ውስጥ መስራት ጀመርኩ። እንደዋዛ ትልቅ ሴት ሆንኩ። ሃያ አንድ ዓመት ሞላኝ በዚህ ወቅት ነው ካሳሁንን ያገኘሁት የሆቴሉ ደንበኛ ነው።
“ቆንጆ እኮ ነሽ እዚህ ቦታ መገኘት አልነበረብሽም::” አለኝ።
“አየህ ተፈጥሮ ቁንጅናን እንጂ የተደላደለ ህይወትን አብራ አልሰጠችኝም::” መለስኩለት።
“የዛሬ ገቢሽን ልስጥሽና እቤትሽ አርፈሽ ተኚ?”
“ይበዛብሃል::”
“እጥፍ ላድርግልሽ!!”
በራሱ መኪና እቤቴ አደረሰኝ።የጠየቅኩትን ገንዘብ ሳያቅማማ ሰጠኝ። በተደጋጋሚ እንዲህ አደረገ። ለዘመናት የሆቴሉ ደንበኛ ሲሆን ከሆቴሉ ሴቶች ጋር ስሙ ተነስቶ እንደማያውቅ ሰማሁ። ከአመታት በፊት ብቸኛ ወንድሙ ከእርሱ ጋር ተጣልቶ በባህር አቋርጦ ወደውጪ ሀገር ሊሄድ ሲሞክር የመሞቱን መርዶ ከሰማ ጀምሮ በየምሽቱ ይመጣል፣ እራቱን ይበላል፣ ይጠጣል፣ ለሴቶቹ ይጋብዛቸዋል፣… … ወደቤቱ ይሄዳል። ከቀናት በኋላ አብሬው እንዳድር በትህትና ጠየቀኝ። እቤቱ ነበር ይዞኝ የሄደው። ከሱ ጋር ካደርኩ በኋላ ወደ ሆቴል ተመልሼ መሄድ አላስፈለገኝም። በየእለቱ ማታ እቤቱ እጠብቀዋለሁ። ሲነጋ ወደቤቴ እመለሳለሁ።
እንዳገባው የጠየቀኝ ቀን እብደት የቀላቀለው ስሜት ነበር የተሰማኝ። ምክንያቱ ባል ማግኘቴ አይደለም። ባል ወንድ ነው ወንድ ደግሞ የገንዘብ ምንጭ ነው። ከዛ ያለፈ አይደለም ለኔ። ካሳሁን ብዙዎች የሚያውቁት ሀብታም ነጋዴ ነው። …… በቃ!! ብር አገኛለሁ። የትኛውም ወንድ እንደሸቀጥ የሚገዛት ሴት መሆኔ ይቀራል፣ እነ አቢዬ ያለስጋት ትምህርታቸውን ይማራሉ፣ በለውጥ ገላዬን እሰጠዋለሁ። ልቤ ያውቀዋል እንደምፈታው። ተጋባን። እህትና ወንድሜን ይዤ እኔ ገንዘብን እሱ ትዳሩን ስንጠብቅ ኖርን።
*
ሳምንታት አለፉ። ሲመቸው ለቤቱ ፕሮሰስ እንደሚመጣ ቢነግረኝም ካሳሁን አልመጣም ። አልደወለም። በቤቱ ምክንያት ቢመጣና ባየው ተመኘሁ።ቤቱ አስክሬን የወጣበት ቤት መስሎ ረጭ አለ።
የቤቱ ድምቀት፡- ትልቅነቱ፣ የቀለማቱ ስብጥር፣ በውስጡ ያጨቀው ውድ እቃ አልነበረም። ሞገሱን ተገፏል። ካሳሁን የለበትም።
የምግቡ ጣዕም የሰራተኛዋ ጥበብ አልነበረም። ከካሳሁን ጋር የምግብ ጠረጴዛው ላይ መታደሙ እንጂ።
የእንቅልፉ መጣፈጥ የአልጋው ምቾት አልነበረም በካሳሁን እቅፍ ውስጥ ማደሩ እንጂ።
ይሄ ሁሉ የገባኝ አምስት ዓመታት ዘግይቶ ሆነ። የህይወት ዘመን ልምዴንና እውቀቴን ያስከነዳው እውነት ካሳሁን ‘ሴት ልጅ ለገንዘብህ ስትል ትወድሃለች’ ብለው እንደሚያስቡ ወንዶች አልነበረም። ገንዘቡን እንደወደድኩት እንጂ ለእሱ ግድ እንደሌለኝ ያውቃል። ራሱን እንድወደው ነበር አምስት ዓመት ሙሉ ሲጥር የነበረው። የፈለግኩትን ሁሉ እንኳን አጊንቼ እሱ ከሌለበት ባዶ መሆኑን ነበር ያሳየኝ። እድሜውን ካፈራው ንብረት እንደበለጥኩበት አሳይቶኝ እድሜዬን ሙሉ የጓጓሁለት ሀብታምነት ከንቱ መሆኑን ነገረኝ። አብሬው ስኖር ያላየሁት እውነት ያ ነበር።
“ ማንም የኔን ያህል አውቆሽ አያውቅም።” ይለኝ ነበር ሁሌም ሳበሳጨው። አሁን ነው ምን ያህል እንደሚያውቀኝ የገባኝ። ባዶነቴ በፍቅር እንጂ በገንዘብ እንደማይሞላ ያውቅ ነበር። እሱ ብቻ ይሄን ያውቅ ነበር።
ስልኬን አንስቼ ደወልኩለት።
“ሰብሊ ይቅርታ ደንበኞች እያናገርኩ ነው። ቆይቼ እደውላለሁ።” ብሎኝ ስልኩን ዘጋው። ‘ቆይቼ’ ያለው ሰዓት ዘላለም መሰለኝ። ሲሊፐር እንዳጠለቅኩ ተነስቼ ከቤት ወጣሁ። እንዲህ ላብድ የሚመስለኝ ሰዓት እብደቴን የማስታግሰው እህትና ወንድሜ ጋር ስሆን ነበር። አሁን እነሱ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች ናቸው። እንድረብሻቸው አልፈልገኩም። ደግሞም ካሳሁንን የአባታቸው ያህል ነው የሚወዱት። በቀስታ እየተራመድኩ ማሰብ ጀመርኩ። አሁን ያለኝን ሁሉ አጥቼ ካሳሁንን ብቻ ማግኘት ተመኘሁ። እግሬን ጭንቅላቴ አላዘዘውም። ወደካሳሁን ቢሮ ሮጥኩ። ርቀቱ፣ አለባበሴ፣ የፀጉሬ መንጨፍረር…….. ምኑም ግድ አልሰጠኝም። ትንፍሼ ቁርጥ ቁርጥ እያለ በሩን ከፍቼ ገባሁ። ሁኔታዬ ያስደነገጣት ፀሃፊው መውጣቱን ነገረችኝ። በደከመ ነፍሴ ወደቤቴ ማዝገም ጀመርኩ። የመጣሁት መንገድ ርቀቱ የታወቀኝ ስመለስ ነው። ብዙ መንገድ ሮጫለሁ። መንገዱ ዳር ድንጋይ ላይ ተቀመጥኩ። ለብዙ ቀናት የረባ ምግብ ያለመብላቴን፣ እረፍት ያለው እንቅልፍ ያለመተኛቴን አሁን ነው ያስታወስኩት። ላዳ ይዤ ወደቤቴ ሄድኩኝ። በሩ ላይ የካሳሁንን መኪና ቆሞ ሳየው ‘እሪሪሪሪረ……’ ማለት አማረኝ። በሩጋ ስደርስ እሱ እየወጣ ነበር። ከላይ እስከታች እያስተዋለኝ
“ስደውልልሽ አታነሺም?”
“ስልኬን ጥዬው ነው የወጣሁት። ቢሮህ እኮ ሄጄ…..”
“አሁን መጥታ ነበር ሲሉኝ ነው ወደቤት የመጣሁት። ሰላም አይደለሽም?” ይዞኝ የመጣው ታክሲ ጥሩንባውን አስጮኸው።
“አልከፈልሽውም እንዴ?” ብሎ እጁን ኪሱ ውስጥ እየከተተ ወደታክሲው አመራ። በዛው የማይመለስ መሰለኝ። ድጋሚ ለሳምንታት የማላየው መሰለኝ
👍4👏1
ምን እንዳደረግኩ የገባኝ ካደረግኩት በኋላ ነው። አፌን ጭንቅላቴ አላዘዘውም።
“እሪሪሪሪሪሪ…….” ብዬ አቀለጥኩት። በታክሲውና በኔ መሃከል ባለ እኩል እርቀት መሃል ደንግጦ ዞረ።
“ምን ሆንሽ?” አጠገቤ ዘሎ ደረሰ። ምን እንደምለው ግን ግራ ገባኝ። የእንባዬ ጠብታ መሬቱ ላይ ተከታተለ። ባለታክሲው በጩኸቴ ተደናግጦ መውረዱን ሳይ ደነገጥኩ።
“ምንም አልፈልግም። ሁሉም ይቅርብኝና አትሂድብኝ!!” እንባዬን እየታገልኩ ያወጣሁት ቃል ይሄ ነው።
“አልሄድኩም እኮ ታክሲውን ልሸኘው ነው::”
“አልፈልግም እኮ ነው የምልህ። ቤቱንም ብሩንም ምኑንም አልፈልግም። ሁሉንም አልፈልግም። አልፈልግም በቃ!!” በእንባዬ ታጅቤ አምባረቅኩኝ።
ያልኩት እንዳልገረመው ፤ እንዲህ እንደሚሆን እንደሚያውቅ ሁሉ ፈገግ እንደማለት ብሎ ወደታክሲው ሹፌር ፊቱን አዞረ። መሬት ላይ እየተንከባለልኩ መጮህ አማረኝ። ብሩን ሰጥቶት ሲመለስ በእንባ በተጋረደ ዓይኔ አየዋለሁ።
“ላቆሰልኩህ ቁስል በሌላ በፈለግከው ነገር ቅጣኝ እባክህ ትተኸኝ አት….” ያልኩትን የሰማ አይመስልም። አጠገቤ ከመድረሱ ከንፈሮቼን ጎረሳቸው።
አምስት ዓመት ሙሉ እንዲህ ነበር የሳመኝ?
▪️አለቀ▪️
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ የኔ ምርጦች
አመሰግናለው🙏
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot ጀባ በሉኝ
“እሪሪሪሪሪሪ…….” ብዬ አቀለጥኩት። በታክሲውና በኔ መሃከል ባለ እኩል እርቀት መሃል ደንግጦ ዞረ።
“ምን ሆንሽ?” አጠገቤ ዘሎ ደረሰ። ምን እንደምለው ግን ግራ ገባኝ። የእንባዬ ጠብታ መሬቱ ላይ ተከታተለ። ባለታክሲው በጩኸቴ ተደናግጦ መውረዱን ሳይ ደነገጥኩ።
“ምንም አልፈልግም። ሁሉም ይቅርብኝና አትሂድብኝ!!” እንባዬን እየታገልኩ ያወጣሁት ቃል ይሄ ነው።
“አልሄድኩም እኮ ታክሲውን ልሸኘው ነው::”
“አልፈልግም እኮ ነው የምልህ። ቤቱንም ብሩንም ምኑንም አልፈልግም። ሁሉንም አልፈልግም። አልፈልግም በቃ!!” በእንባዬ ታጅቤ አምባረቅኩኝ።
ያልኩት እንዳልገረመው ፤ እንዲህ እንደሚሆን እንደሚያውቅ ሁሉ ፈገግ እንደማለት ብሎ ወደታክሲው ሹፌር ፊቱን አዞረ። መሬት ላይ እየተንከባለልኩ መጮህ አማረኝ። ብሩን ሰጥቶት ሲመለስ በእንባ በተጋረደ ዓይኔ አየዋለሁ።
“ላቆሰልኩህ ቁስል በሌላ በፈለግከው ነገር ቅጣኝ እባክህ ትተኸኝ አት….” ያልኩትን የሰማ አይመስልም። አጠገቤ ከመድረሱ ከንፈሮቼን ጎረሳቸው።
አምስት ዓመት ሙሉ እንዲህ ነበር የሳመኝ?
▪️አለቀ▪️
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ የኔ ምርጦች
አመሰግናለው🙏
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot ጀባ በሉኝ
👍13
#አንድ_ነን
ጠረኔ ሲሸተኝ፤ጠረንህ መሰለኝ
ፊቴን ስዳብሰው፤ፊትህን መሰለኝ
አይኖቼን ሳሻቸው፤ አይኖችህ መሰሉኝ
የራሴው ጆሮዎች፤ የራስህ መስሉኝ
አንድ ነገር ግን፤የኔ የሆነው
ያንተ አልመስልሽ አለኝ
ከሁሉ ነገሬ፤እሱ ግን ቀረብኝ
ትለኝ እንዳልነበር
እኔ ማለት አንቺ፤አንቺ ማለት እኔ
ልዩነት የለንም፤ አንድ ነን ሄዋኔ
ትለኝ እንዳልነበር
ታዲያ ምን ለየው፥መልስልኝ ፍቅሬ
ብዬ ስጠይቅህ፤ገረመኝ ምላሽህ
ድስትና ግጣሙ
የተጋጠሙት፤ልዩ ቢሆኑ ነው
አንድ ላይ የሆኑት
እኔ ማለት አንቺ፤አንቺ ማለት እኔ
በእርግጥም ልክ ነው፤እውነት ነው ሄዋኔ
ፆታችን ቢለያይ፤ምንም አይግረምሽ
ሁልጊዜም አንድ ነው
ነገሬ ነገርሽ፤እንደዚያ ስኖን ነው
እንደ ድስቱ እና፤ ክዳኑን ምንሆነው
አቻም የምንሆነው
ጠረኔ ሲሸተኝ፤ጠረንህ መሰለኝ
ፊቴን ስዳብሰው፤ፊትህን መሰለኝ
አይኖቼን ሳሻቸው፤ አይኖችህ መሰሉኝ
የራሴው ጆሮዎች፤ የራስህ መስሉኝ
አንድ ነገር ግን፤የኔ የሆነው
ያንተ አልመስልሽ አለኝ
ከሁሉ ነገሬ፤እሱ ግን ቀረብኝ
ትለኝ እንዳልነበር
እኔ ማለት አንቺ፤አንቺ ማለት እኔ
ልዩነት የለንም፤ አንድ ነን ሄዋኔ
ትለኝ እንዳልነበር
ታዲያ ምን ለየው፥መልስልኝ ፍቅሬ
ብዬ ስጠይቅህ፤ገረመኝ ምላሽህ
ድስትና ግጣሙ
የተጋጠሙት፤ልዩ ቢሆኑ ነው
አንድ ላይ የሆኑት
እኔ ማለት አንቺ፤አንቺ ማለት እኔ
በእርግጥም ልክ ነው፤እውነት ነው ሄዋኔ
ፆታችን ቢለያይ፤ምንም አይግረምሽ
ሁልጊዜም አንድ ነው
ነገሬ ነገርሽ፤እንደዚያ ስኖን ነው
እንደ ድስቱ እና፤ ክዳኑን ምንሆነው
አቻም የምንሆነው