አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
571 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
“ስለ እኔና ስለ ዉብርስት ነው እንዴ ጉዳዩ ጭራሽ?” አለ ባልቻ፣ በአንድ ዓይኑ ወደኔ እየሰረቀ፡፡ እሱም ስለ ምን እንደሚብከነከኑ እስከ አሁን አልገባዉም ኖሯል።

“እናንተ ናችሁ እንጂ ሌላማ ማን እንዲህ ጉድ ይሠራኛል?”

“እባክዎ በግልጽ ይንገሩን፣ ምን አጉድለን ነው?”

“ምናለበት እንደ ወጉ እንኳን ብታደርጉት? በዚያ ዓይን ከተፈላለጋችሁ በሥርዓቱ እንዳትጋቡ የሚከለክላችሁ አልነበረ! ለምን የኃጢአቱን
መንገድ መረጣችሁት ባልቻ?”

“ምንም ሊገባኝ አልቻለም ዛሬ” አለ ባልቻ፣ ወደኔ መዞር እየሰለቸው። እኔ ግን እየገባኝ መጥቷል። የኔው ጉድ ነው። ደርሶ ሆዴን ገዘገዘኝ። አመመኝ፡፡

“አይደል” አሉ፣ የቅድሟን ለበጣ መልሰዉ እያመጧት። “መቀባባቱ
እንኳ ባንተ ይቅርና በሌላውም አያምር። ይልቅ እሱን ተወዉ፣
እንዳይለምድብህ። ለመሆኑ ምን ያህል ጊዜ ሆነው?”

“ባዛኝቷ! የምኑ?” አለ ባልቻ፣ በንዴት እየተስተካከላቸው፡፡

“ሃያ ሳምንት!” አልሁኝ፣ ከአፋቸው ነጥቄ፡፡ ሳይታወቀኝ ደረቅ ቁጣ
አንቆኛል፡፡ በእኔም ብሶ ደግሞ እንደ አሮጌ ቆርቆሮ ነው የጮህኩት። “ሃያ ሳምንት ከአራት ቀን!” አልኋቸው፣ የባሰ እየተንኳኳሁ። የባልቻ ያላ
ኃጢአቱ መጠርጠር ሁሉ ግድ አልሰጠኝም። ወንበሩን ወደ ኋላ
አሽቀነጠርሁና፣ እየተቆናጠርሁ ወደ በሩ ሄድሁኝ፡፡ በሩን በኃይል በርግጄ ከከፈትሁ በኋላ፣ ግው አድርጌ ዘግቼባቸው ወጣሁ። ምን እየሆንሁ እንደሆነ እንኳን እነሱ ለኔም አልታወቀኝም፡፡....

ይቀጥላል
👍18
#ምንዱባን


#ክፍል_አርባ_አራት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

...እውነትም ቦታው እስትራቴጂካዊ ነበር በአንድ በኩል ወደቤቱ ሚያስገባው መንገድ ሰፊ ነው:: በጓሮ በኩል ቀደም ሲል እንደተገለጸው ቀጭን የጨለማ መንገድ አለው:: ማንኛውም አጥቂ ጦር በሴንት ዴኒስ
ጎዳና በኩል ባለው ሰፊ ጎዳና እንጂ በጓሮ በኩል ደፍሮ ሊገባ አይችልም::ስለዚህ የፊት ለፊቱን አጥብቀው ከያዙ የኋላውን በቀላሉ መመከት ይቻላል።
ድንገት ማፈግፈግም ቢመጣ በጓሮ በኩል የማምለጥ እድል አለ::

ያ ሁሉ ሕዝብ ሆ እያለ መለስ ሲል መንገዱ ሁሉ ጨነቀው::
ባለሱቅ ቶሎ ብሎ ሱቁን ዘጋ:: ከግራና ከቀኝ የነበሩ ሴቶች ሁሉ የውጭ በር ካላቸው የውጭ በራቸውን፣ አለዚያም የየቤታቸውን በርና መስኮት ቀረቀሩ፡፡ ለወሬ ሞትኩ ባይ መስኮቱን ከፍቶ በትንሹ ያያል፡፡ አላስችል
ያለውና «ምን ይቀርብኛል ብሎ ተስፋ የቆረጠው ከሰልፈኛው ጋር
ይደባለቃል፡፡

አንዲት በጣም የተደናገጠች አርጊት ምን አደረገች? ቶሎ ብላ አሮጌ ፍራሽ ከውጭ በኩል በገመድ በማንጠልጠል መስኮትዋን ሸፈነችው:: ሌላ
ፍራሽ ደግሞ ከውስጥ በኩል በማቆም ጋረደችው፡፡ ከዚያም ከመስኮቱ በር ወለል ላይ ለጥ ብላ ተኛች:: ጥይት ሲተኮስ እንዳይመታት ነበር፡፡

በዚያ አካባቢ በርና መስኮቱ የተከፈተ ቤት ሲኖር ያ መሸታ ቤትና ምግብ ቤት ብቻ ነበር:: ይሄ ደግሞ ያለ ምክንያት አልነበረም:: ትርምሱ፣ ጩኸቱ፣ ስድቡና
መዝሙሩ ድብልቅል ያለ ስለነበር የምጽዓት ቀን የመጣ
ስላስመሰለው ነው::

“ወያኔ ፣ ወይኔ፣ አምላኬ የዛሬን! ከዛሬው ብቻ ሰውረኝ» አሉ ማዳም ኻሽሉፕ ፡
ወዲያው በሃያ ደቂቃ ውስጥ ከሴትዮዋ መጠጥና ምግብ ቤት ምሽግ ተሠራ፡፡ በርሜሎች ተለቃቅመው በአሸዋና ጠጠር ተሞሉ፡፡ ጋብሮች በርሜል በማንከባለል ረዳ፡፡ በርሜል ሊሸፍነው ያልቻለውን ቦታ በአፈርና
በድንጋይ ቁልል ታጠረ፡፡ ኤንጂልራስ በጓሮው በኩል ወዳለው ጨለማ መንገድ የሚወስደውን በር ወለል አድርጎ ከፈተው:: ከዚያም ከቤቱ በር
ወደሚገኘው እቃ ማስቀመጫ ክፍል ወረደ:: ከምድር ቤቱ ውስጥ ወደሚገኘው ጥቂት በርሜሎችን አገኘ፡፡ እነርሱንም ለምሽግ ሥራ ተጠቀሙባቸው::መቼም እጅ ከተባበረ የማይሠራው ሥራ የለምና «ብዙ ቀናት ፈጅቷል
ተብሎ ሊገመት የሚችል ምሽግ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀቀ፡፡ በዚያች አጭር ሰዓት ያ ቤት ከቡናና ምግብ ቤትነት ወደ ጦር ካምፕ ተሸጋገረ::

አንድ ጋሪ ሴቶችን ጭኖ በዚያ በኩል ለማለፍ ይመጣል፡፡ ከሰልፈኞቹ መሪ አንደኛው ሮጦ ሄዶ ባለጋሪውንና ሴቶችን ካስወረደ በኋላ ሴቶቹን
ከይቅርታ ጋር አሰናበታቸው:: የፈረሱን ልጓም ይዞ በመጐተት ጋሪውን ወደ ምሽጉ ወሰደው::

«ጋሪ ደግሞ በዚህ ሰዓት፣ በዚህ መንገድ ምን ያደርጋል?» ሲል
ጠየቀ፡፡ «ከአሁን ቀደም በዚህ መንገድ ጋሪ አልፎ አያውቅም» ብሎ ከተናገረ በኋላ ፈረሱን ከጋሪው አላቅቆ አባረረው:: ፈረሱ ከሄደ በኋላ ጋሪውን በጎን
በማጋደም ያንን መንገድ ለመዝጋት ተጠቀመበት::

ማዳም ኸሽሉፕ ተናደዱ፣ የሚያደርጉትን ስላጡ ከአንደኛው ፎቅ ቁጭ ብለው ቀሩ፡፡ ዓይናቸው ከወዲያ ወዲህ ይቅበዘበዛል፡፡ፀ ሳይታወቃቸው እንባቸው በጉንጫቸው እንደ ጎርፍ ይወርዳል፡፡ ድምፅ አሰምተው ለማልቀስ ተሰብረዋል
አልደፈሩም::

«ምፅዓት ነው ይሄ» ሲሉ አጉረመረሙ::

ከሰካራሙ አንደኛው መጥቶ ጉንጫቸውን ከሳመ በኋላ «መቼም
እንደ ሴት ጉንጭ የሚለሰልስ ነገር የለም» ይላል፡፡

ቫውደር የተባለች ሠራተኛ እነርሱ ከነበሩበት ክፍል ገባች:: ከሰካራሞች ሌላው በሳቅ እየተፍነከነከ የሴትዮዋን ጨርቅ በመጎተት ወደ መስኮት
ወሰዳቸው:: ወደ ጆሮአቸው ተጠግቶ አናገራቸው::
«ቫውደር እኮ በጣም ፉንጋ ናት:: መቼስ ለፉንጋዎች ምሳሌ ሆና |
ልትቀርብ የምትችል ናት:: »

ወዲያው ኤንጆልራስ ጮክ እያለ ተናገረ፡፡

«እናንተ ሰካራሞች የምሽጉን ስም አታጉድፉ:: ቶሎ እንዲበርድላቸው

ከዚህ ሂዱና ከምትተኙበት ተኙ፡፡ ይህ ሥፍራ በአገር ፍቅር ለነደዱ እንጂ ለሰካራሞቹ አይደለም

ከሰካራሞቹ ማለትም ብዙም ያልጠነበዘው በዚህ ስድብ
ከተሞላበት ንግግር ስሜቱ በጣም ስለተነካ ውሃ በጣሳ አንስቶ ፊቱ ላይ ቸለበሰ፡፡ የውሃው ቅዝቃዜ እውነትም ስካሩን ትንሽ አበረደለት:: ወደ መስኮቱ ሄዶ ኢንጆልራስን ጥያቄ ጠየቀው::

«ከዚሁ ልተኛ?»

የለም፣ ከምትተኛበት ሂድና ተኛ እንጂ ከዚህ መተኛት አይቻልም::»
«እባካችሁ ነፍሴ እስክትወጣ ከዚሁ ልተኛ» ሲል ሰካራሙ በለዘበ አነጋገር ተናገረ፡፡

ኢንጆልራስ በንቀት ዓይን አየው:: ሰካራሙም የሚባለውን ሳይሰማ
ጥቂት ከተንተባተበ በኋላ አጠገቡ ከነበረው ጠረጴዛ ላይ ጭንቅላቱን አስደግፎ ብዙም ሳይቆይ እንቅልፍ ይዞት ጭልጥ አለ፡፡ቸ

ዝናቡ ቆሞአል፡፡ ተጨማሪ ሰልፈኛ የተለያየ መሳርሪያ እየያዘ መጣ፡፡
በሩቁ የምትታይ አንዲት የመንገድ መብራት ብቻ ነበረች:: እስዋም ብዙ አልቆየችም፤ ሰልፈኞቹ ሰበርዋት:: የተቀሩት መብራቶች ቀደም ሲል
ተሰብረዋል፡፡

ኢንጆልራስ፣ ካምብፌራና ከርፌይራክ ለሰልፈኛው አመራር መስጠት ጀመሩ፡፡ መንገዱ በሁለቱም አቅጣጫ በምሽግ ተዘጋ:: የጦር መሣሪያ የያዙ
ሁሉ ቦታ ቦታቸውን ያዙ:: አንዳንዶቹ ቆብ መሳይ ነገር አጥልቀዋል::አንዳንዱ በአጭር ታጥቆ ጎራዴ ሲይዝ ሌላው ጠብመንጃ አንግቷል።
መሣሪያ ይዞ ፈረስ ላይ የተቀመጠም አለ፡፡ አንዳንዱ የመጨረሻው ሰው እስከቀረ ድረስ እንዋጋለን» እያለ ይፎክራል፡፡ ሌላው ጥይት ሲያልቅ
በድንጋይ እንማታለን» ይላል:: አንዱ ያቅራራል፣ ሌላው ይሸልላል::አንዳንዱም እነርሱ ሲጠቁ የከተማው ሰው እንደሚደርስላቻው እርስ በእርስ
ይወያያል፡፡ ሁሉም በየፊናው ይነጋገራል፤ ይቻኮላል፤ ሥራ ለመሥራትና ቦታ ለመያዝ ይጣደፋል፡፡ ሰካራሞቹና የቡና ቤቱ ባለቤት የሚያደርጉትን
አጥተው ከአንድ ክፍል ውስጥ ተፋጥጠው ቁጭ ብለዋል::
ከቁመቱ፡ ዘለግ ያለውና የሰልፈኛው መሪ የሆነው ሰው ከሰልፈኛው መካከል ገብቶ ምሽግ ይሠራል:: ጋብሮችም ከምሽጉ ጫፍ ላይ ከወዲያ ወዲህ ይሯሯጣል:: ማሪየስን የጠየቀውና ኩርፊያሪክን ጠብቀኝ
ያለው የሴት መልክ ያለው ግለሰብ ግን ከዚያ አልነበረም፡፡ ጋብሮትች
ከደስታው ብዛት ከወዲህ ወዲያ የሚለው እየዘፈነ ስለነበር አብዛኛው ሰልፈኛ ለይቶታል:: እንዲያውም ከነአካቴው ሰው ሁሉ የእርሱን ንቃትና ሞራል እያየ በጣም ተደፋፈረ፣ ሰነፉንና ዳተኛውን አነቃቃ:: ለፈሪውም
ልብ ዋጀለት። ለተደነባበረውም መንገድ ከፈተለት።

ጋብሮች ከአሮጊትዋ በነጠቀው ሽጉጥ ስላልረካ «ጠብመንጃ
እፈልጋለሁ፣ ምነው ብትሰጡኝ» እያለ ይጠይቃል::

«ጠብመንጃ ለአንተ ነው ወይስ ለማነው?» ሲል ካምብፌሪ ጠየቀው
«ምነው?» ሲል ጋብሮች ጥያቄን በጥያቄ ይመልሳል፡፡ «ምን ይጉድለኛል? ድሮ እኮ እንዴት ያለ ጠብመንጃ ነበረኝ» ሲል ይሸልላል::
ኢንጆልራስ ይስቃል፡፡
«አዋቂዎቹ ሲዳረሳቸው ለልጆች ይሰጣል::»
ጋብሮች በቁጣ ዞር ብሎ ይመልሳል፡፡
«አንተን ከእኔ በፊት ከገደሉህ እኔ እኮ ነኝ አንተን የምተካው:: ላከወ
«ጉረኛ» ሲል በቀልድ መልክ ኢንጆልሪስ መለሰለት::

«ጉረኛ አልከኝ?» ሲል ጋቭሮች ቃሉን ደገመ:: ይህን እንደጠየቀ
አንድ ሰው ከሰልፉ ወጥቶ ያያል:: ሮጦ ሄዶ «ከሰልፈኛው ተለይተው
አይሄዱ፤ ለዚህች ምስኪን አገር የሚውሉት ውለታ ቢኖር አሁን ነው፤ ስለዚህ አይሂዱ» ሲል ይማጠናቸዋል፡፡ ሰውየው ግን ፈጠን ብለው በመራመድ
ይሄዳሉ፡፡
👍12
የአንዳንዶቹ ምሽግ እስከ ሁለት ሜትር ከፍታ ነበረው፡፡ ስለዚህ
ተዋጊዎቹ ከፈለጉ ከምሽጉ ኋላ ሊደበቁ ወይም እየተዋጉ ራሳቸው
ሊመክቱበት ይችላሉ:: ከተሠሩት ረዣዥም ምሽጎች መካከል በአንድ አንድ ሰው ብቻ ሊያሳልፍ የሚችል ክፍት ቦታ አልፎ አልፎ ይታያል ከምሽጎቹ አናት ላይ ቀይ ጨርቅ ተሰቅሎአል:: ከመጠጥ ቤቱ ጀርባ ያለው ምሽግ ጨርሶ አይታይም።

ከመጠጥ ቤቱ አንድ ጠረጴዛ ከወጣ በኋላ ኢንጆልራስ ከጠረጴዛው ላይ ወጣ:: አንድ ትልቅ ሳጥን ከእግሩ ስር አስቀመጡለት:: ሳጥኑ ተከፈቱ
በጥይት የተሞላ ነበር፡፡ ጥይቱን ከምሽግ ዘሪያ ለተቀመጠ ተዋጊ አከፋፈለ፡፡ እያንዳንዱ ሰወ ሰላሣ ጥይት ደረሰ::: ተዋጊች
ጠብመንጃዎቻቸውን አጎረሱ፡፡ መንገዱ ሁሉ ረጭ አለ፡፡ ከዚያ አካባቢው አንድ ድምፅ አይሰማም::

ሁሉም ሰው «ቀጥሎ ምን ይሆን?» እያለ ይጠባበቃል፡፡ ቀኑ እየጨለመ ሄደ:: ምሽጉ ውስጥ ከተቀመጡት ሰዎች መካከል አንዳንዶቹ መብራት አበሩ፡፡ ጊዜው እየገፋ ሄደ፡፡ አሁንም ምንም ነገር የለም፣ የመንግሥት
ወታደሮች ከፍተኛ ዝግጅት ላይ እንደሆነ የአድማው መሪዎች ጠረጠሩ፡፡ እነዚያ ጥቂት ሰዎች በብዙ ሺህ የሚቆጠር የመንግሥት ሠራዊትን ነበር
የሚጠብቁት::

ኤንጆልራስ ጋብሮችን ፍለጋ ሄደ፡፡ ጋቭሮች ከምድር ቤት ውስጥ
ተቀምጦ ሥራ እየረዳ ነበር:: ያ ከወደኋላ መጥቶ ከሠራዊቱ ጋር
የተደባለቀው ረጅሙ ሰውዬም ከዚያው ነበር፡፡ ጋቭሮች ግን ልብ አላለውም፤ ምክንያቱም ይህ ሰው ጠብመንጃውን ይዞ የተቀመጠው ጨለም ካለ ሥፍራ ላይ ነበር፡፡ ሰውዬው በአሳብ ተውጦ የሚሆነውን ሁሉ ተግራ ተቀኝ እያለ ያጤናል::

ኢንጂልራስ ወደ ጋቭሮች ጠጋ ብሉ «ትንሽ ልጅ ስለሆንክ አንተን
ማንም ልብ አይልህምና ቶሎ ብለህ ወደ ዋናው ጎዳና ብቅ በል፡፡ ከዚያ የሚሆነውን በሚገባ ካጤንክ በኋላ ምን እንዳለ ተመልሰህ ንገረኝ ብሎ ላከው::

ጋብርች ኢንጆልራስን ቀና ብሉ አየው::

«ትንንሽ ሰዎችም ይጠቅማሉና» ካለ በኋላ «ይህማ ለክፉ አይሰጥም፣ ደህና ነው:: ሄጄ ወሬ ቃርሜ እመጣለሁ:: ግን ይገርማል፤ ትንንሽ ልጆች
ሲታመኑ ትልልቆቹ ለምን አይታመኑም?» ብሎ ይጠይቃል፡፡
ጋቭሮች ለመውጣት አንገቱን ቀና ሲያደርግ ያንን ግዙፍ ሰው
አየው፡፡ «ያንን ሰው ታዩታላችሁ?» ብሎ ጣቱን እየቀሰረ ያሳያል፡፡
«ያ ጠመንጃ ይዞ የተቀመጠው» ሲሉ ጠየቁት::
ለጥያቄው መልስ ሳይሰጥ «ሰላይ ነው» ይላቸዋል፡፡
«እርግጠኛ ነህ?» ሲሉ ጠየቁት::
«ሁለት ሳምንት አይሞላውም ጆሮዬን ቆንጥጦ ከጎተተኝ::
ኢንጂልራስ ድምፁን ዝቅ አድርጎ ለነበረው ሰው አንድ የሆነ ነገር
ነገረው:: ሰውዬው ከዚያ ወጥቶ ሄደ:: ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ሌሎች ሦስት ሰዎችን ይዞ ተመለሰ፡፡ አራቱ ዕዎች በማያስነቃ ሁኔታ ቀስ ብለው ሰውዬው ተቀምጦበት ከነበረው ሥፍራ በተለያየ አቅጣጫ ሄደው ከብበውት ቆሙ፡፡

በዚህ ጊዜ ኢንጂልራስ በቀጥታ ሄዶ ሰውዬውን አነጋገረው::

«ማነህ አንተ» ሲል በድፍረት ጠየቀው::

በዚህ ባልተጠበቀ ድንገተኛ ጥያቄ ሰውዬው በመጀመሪያ እንደመደንገጥ አለ፡፡ አንገቱን ሳይሰብር የኢጆልራስን ዓይን እያየ በቆራጥነትና በሚያስጠላ
ፈገግታ ፊቱን አስውቦ በድፍረት መልስ ሰጠው::

«ሥራችሁና ዓላማችሁ ምን እንደሆነ ተረድቼዋለሁ፡፡»
«ሰላይ ነህ አይደል?»
«አዎን፣ የመንግሥት ባለሥልጣን ነኝ»
«ማነው ስምህ?»
«ዣቬር እባላለሁ፡፡»
ኢንጂልራስ ለአራቱ ሰዎች ምልክት ሰጣቸው፡፡ ከመቅጽበት ሰዎች ዣቬር ላይ ተረባረቡ፡፡ ወዲያው ዣቬር ፊቱን አዙሮ ማየት እንኳን ጊዜ ሳያገኝ አንቀው ይዘው እጅ እግሩን ጠፍረው አሰሩት፡፡ እጁን የፍጥኝ ካሰሩ በኋላ መላ ሰውነቱን ፈተሹ፡፡ ከቋሚ የብረት ግንድ ጋር አሠሩት::
ጋቭሮች የተደረገውን ሁሉ ቆሞ ተመለከተ፡፡ ይህ ሰው ቀደም ብሎ
ለመምሰል የበደለው ስለነበረ በድርጊቱ አንጀቱ ራሰ፡፡ ወደ ዣቬር ጠጋ ብሎ « ድመት በአይጥ ተያዘ» አለው::

«ዣቬር ይህ ሁሉ ሲሆን ድምፅ አላሰማም፡፡ ከቋሚ ብረት ጋር
በመታሠሩ መነቃነቅ አይችልም፡፡ እነኩርፌይራክና ኮምብፌሬ ተመለከቱት።
«ሰላይ ነው» ሲል ኢንጆልራስ ኋላ ለመጡት ጓደኞቹ አስረዳቸው::
ወደ ዣቬር ዞር ብሉ «ምሽጋችን ከተያዘ ትገደላለህ» አለው::
«ለምን አሁኑኑ አትጨርሱኝም» ሲል ቁጣ በተሞላበት እንደበት
ዣቬር ጠየቃቸው::
«ጥይት እንዳይባክን» ሲሉ መለሱለት::
«ለምን በቢላዋ አንገቴን አትቆርጡትም፡፡»
«አንተ ሰላይ» አለ መልኩመልካሙ ኢንጆልራስ፡፡ «እኛ ዳኞች ነን እንጂ ቅጥር ነፍሰ ገዳዮች አይደለንም፡፡»
ከዚያም ጋቭሮችን ጠራው፡፡
«አንቺ፣ ሂጅና የተላክሽበትን ፈጽሚ፡፡ የነገርኩርህን ፈጽመህ በቶሎ ተመለስ፡፡»
«መሄዱ ነው» ብሎ ጮክ ብሎ ተናገረ፡፡....

💫ይቀጥላል💫
👍14😁1
#ገረገራ


#ክፍል_ሶስት


#በታደለ_አያሌው


...“ሃያ ሳምንት!” አልሁኝ፣ ከአፋቸው ነጥቄ፡፡ ሳይታወቀኝ ደረቅ ቁጣ አንቆኛል፡፡ በእኔም ብሶ ደግሞ እንደ አሮጌ ቆርቆሮ ነው የጮህኩት። “ሃያ ሳምንት ከአራት ቀን!” አልኋቸው፣ የባሰ እየተንኳኳሁ። የባልቻ ያላ
ኃጢአቱ መጠርጠር ሁሉ ግድ አልሰጠኝም። ወንበሩን ወደ ኋላ
አሽቀነጠርሁና፣ እየተቆናጠርሁ ወደ በሩ ሄድሁኝ፡፡ በሩን በኃይል በርግጄ ከከፈትሁ በኋላ፣ ግው አድርጌ ዘግቼባቸው ወጣሁ። ምን እየሆንሁ እንደሆነ እንኳን እነሱ ለኔም አልታወቀኝም፡፡

መኪናዬ ዉስጥ ገብቼ እንዴት አድርጌ በየት በኩል እንደ ነዳሁት
አላስታውሰውም፡፡ እንዲሁ ብዥ እንዳለብኝ ወደ ራሴ ቤት የሚወስድ በመሰለኝ መንገድ የእውር ድንብሬን እያሽከረከርሁ ነበር፡፡ ገና ትንሽ እንደ ነዳሁ፣ ሁሉም ነገር ሰለቸኝ፡፡ ጠነባኝ፡፡
ይበልጥ ድቅድቅ ብሎ ጨለመብኝ፡፡ እንደ ምንም ዳር ይዤ አረፍ አልሁና ወደ ልቡናዬ
ለመመለስ ረዥም ጸሎት አደረስሁ፡፡ ሻል እንዳለኝ፣ የተሻለ ቦታ ተከሰተልኝ፡፡ የእናቴ ቤት!
የመኪናዬን መሪ በግራ በኩል ጠመዘዝሁት እና ወደ እመዋ ቤት
የሚወስደዉን መንገድ ተያያዝሁት። እግዚአብሔር ከክፉ አደጋ ጠብቆኝ በደህና ደረስሁ እንጂ፣ አኳኋኔ እንኳን አያድርስ ነበር። ወደ እመዋ ቤት ደርሼ ስገባ ግን ማንንም አላገኘሁም፡፡ ባዶዉ ቤት ሊዉጠኝ አፉን አ ብሎ
ከፍቶ ጠበቀኝ፡፡ ይኼ ሰፊ ቤት አሁንም አሁንም እንባዉን እስከማዉቅለት ድረስ አዛጋብኝ፡፡ እንደ ገና ደግሞ ሊያስገባኝ የቀፈፈውም መሰለኝ፡፡ እንደ
ምንም ወደ ዉስጥ ብዘልቅም፣ በዚህ ቀትር እንደ እኩለ ሌሊት ነው የጨላለመብኝ፡፡ እግሬን እየጎተትሁ ግራ ቀኝ ከተቅበዘበዝሁ በኋላ፤
ለሳሎኑ ወደሚቀርበዉ ክፍል ገብቼ አልጋዉ ላይ ወደቅሁበት።

ጥቅልል ብዬ መተኛት ነበር የሚሻለኝ፡፡ እንቅልፍ ግን ከየት አባቱ ይምጣልኝ? ነገሩ ሁሉ ተደበላልቆብኛል፡፡ እህል የሚባል ለመጨረሻ ጊዜ የቀመስሁት ትናንትና ማታ ነው:: ግን አሁንም አልራበኝም። ለነገሩ፣ እንደ ሥራዬ ቢሆንማ፣ እንኳንስ እመዋ ቤት ይቅርና እመዋ የረገጠችው
አፈር ላይ እንኳን የመተኛት ሞራሉ የለኝም፡፡ በዚያም ላይ ይኼ አልጋ
ጠዋት ከእመዋ ጋር በታዕካ ነገሥት ገዳም ቆይቼ ስወጣ መንገዴ ላይ ቆመዉ እህቱ አይደለችም ብለዉ የተወራረዱበት፣ የወንድሜ የጃሪም አልጋ ነዉ።

ሁሉንም ነገር ማፈር ጀምሬያለሁ።

የአባቴ ነፍስ እንዴት ትጠየፈኝ ይሆን? የየዋኋ እናቴ አምላክስ እንዴት ይጠላኝ ይሆን? እያልሁ ተበጠበጥሁ። ይኼ አልበቃ ብሎኝ፣ ከአንድ መቶ አርባ አራት ቀናት በፊት የተፈጠረው ነገር ሁሉ በዓይነ ኅሊናዬ እየተመላለሰ ዕረፍት የሚባል ነገር ከለከለኝ፡፡ ላለማስታወስ ከራሴ ጋር
ብዙ ብቦቃቀስም፣ አለማስታወስ ግን አልቻልሁም፡፡ ዕለቷ ከነቅጽበቷ ሳትቀር መጥታ የሚከብድ ጥላዋን ጥላብኝ ዓይነ ልቡናዬ ላይ ቁጭ አለችብኝ፡፡

ትዝ አለኝ።

ዕለቷ እሁድ ነበረች። በዚያች ዕለት፣ አመሻሽ ላይ እንደ ልማዴ ክራሬን ይዤ ወደ አንድ ምዕራባዊ የአዲስ አበባ ዳገታማ ሥፍራ ላይ ወጥቻለሁ። ልክ እንደ ሁልጊዜው፣ ከሚወዱኝ የቀረ ሰው አልነበረም። ጠይም ወይ ቀይ፣ ያገባ ወይ ያላገባ፣ ወንድ ወይ ሴት፣ የወለደ ወይ ያልወለደ፣ አማኝ
ወይ ከሃዲ ሳይቀር ግልብጥ ብሎ ከቦኛል። አንዳንዱ መልኬ ጠርቶት፣ አንዳንዱ ድምፄ ናፍቆት፣ አንዳንዱ ደግሞ ሌላ ሰው ተከትሎ መጥቷል። አለባበሴም ፀሐያማ ነበር።

አስታዉሳለሁ።

ዉቧ ጀንበር ሄድሁ ሄድሁ ብላለች፡፡

ሲጀመር ለፀሐይ ምንም አይወጣላት። ለኔ ደግሞ ምንም ሲሆን፣ ከዚህ ሰዓት ሌላ ዉበቷ ደምቆ አይታየኝም። በአድማሱ ላይ እግሮቿን ከፋፍታ፣ ደልቀቅ ብላ የምትታየኝ ሲመሻሽ ብቻ ነው፡፡ ነፃነቷስ! ራሷን ወደ ታች
በምድር ላይ፣ እግሯን ደግሞ ወደ ላይ በሰማዩ ትሰቅለዋለች። መዘቅዘቋን ተከትሎ፣ ስስ ፀሐያማ ቀሚሷ ገለብ ቢልም፣ ሐፍረተ እንትኗን ግን አናይባትም፡፡ የእኔን ጉጉት እያየች ነዉ መሰለኝ፣ ፈገግ ትልብኛለች።ፈገግታዋ ደግሞ በማንም ቆዳ ላይ አይደርስም፡፡ ይኼ ራሷ ለራሷ የሰጠችው የፍስሐ ጊዜዋ ይመስለኛል። ባትሞት ትታመም፣ ሥጋ
የሚባል ግን አይኖራት ይሆን?
በዚሁ ዕለትም ከጀንበሯ ፈገግታ ፊት ለፊት ሆኜ የግራ እጆቼን ጣቶች በክራሬ አዉታሮች ላይ ዘርግቻለሁ። ከዚያም ምዕራብ ምዕራቡን እያየሁ፣
ለስለስ አድርጌ መግረፍ ጀመርሁ።

ደገኛዉ መጽሐፍ
ባሪያዎችህም ጭምር፣
ኢትዮጵያን ይሏታል
ጌታ ያንተ ሀገር።
እንግዲያዉ ጌታዬ፤
አልሟገትህም
ሀገሬን ወደ ጫፍ ሲገፉት ብትል ዝም፣
ባገርህ ነኝና ካንተ አይብስብኝም።

ድምፄን ጨመር አድርጌ እንደ ገና አንጎራጎርሁ።

ጌታ በናትህ መልሰው፣
እረ ጌታ በማርያም መልሰው
የጀግናዬ ን ልብ እንደ ሰው።

ይኼንን ብዬ፣ ያለ ልማዴ እንደ አጋጣሚ ቀና ብል፣ ከመካከላቸው አንድ ወጣት ሹልክ ብሎ ሲሄድ አየሁት። የከበበኝን ሰዉ ሁሉ ከምንም ሳልቆጥር በረቃቅሼዉ ብድግ ብዬ ተከተልሁት። ይኼን ልጅ ነው ለመጀመሪያም ለመጨረሻም ጊዜ
ነፍስ የተያየሁት፡፡ ይኼን ልጅ
እስከማውቀው ድረስ ዕለት በዕለት የምቆጨው መነኩሴ ባለመሆኔ ነበር።በተለይም ልጅ እያለሁ ካህኑን አባቴን ተከትዬ ለመሳለም ወደ ገዳም በምሄድ ጊዜ፣ ለደስታዬ ወደር አልነበረውም፡፡ ከዛሬ ነገ ገዳም ገብቼ በአመክሮ እጀምራለሁ እያልሁ ቀን እቆጥራለሁ። አባቴ እና እናቴ እንኳን ከእኔ የሕይወት መስመር በቀር የሚያከራክራቸው ጉዳይ መኖሩን አላዉቅም። አባቴ ሁልጊዜም ቢሆን ዉብርስቴ መንኩሳ እስከ እመምኔትነት ደርሳ ሳታሳየኝ አልሙት» የሚል ነበር ጸሎቱ ሁሉ። እናቴ ደግሞ በተቃራኒዉ ልጄ ማለፊያ ትዳር ገብታ ዓይኗን በዓይኗ ሳታሳየኝ
አትግደለኝ ባይ ናት። እንዲያዉ ድከሙ ቢላቸዉ ነዉ እንጂ፣ እመዋ ሆኖላት አባቴን እንዴትም ብላ ብታሳምነዉ እንኳን፣ የእኔ ዝንባሌ ግን የአባቴ ምርጫ ነበር። እማሆይነት። ቢሆንልኝ ብዬ የምመኘዉን የምንኩስና ስም ሁሉ ለራሴ አዉጥቼ አዉቃለሁ። አብዝቼ የተለማመድሁት ሕይወትም ምንኩስናን ነዉ። እጅግ በጣም የምቀናባቸው ሰዎች፣ በአርምሞ ዉስጥ ያሉ መነኮሳት ብቻ ናቸዉ።
በሕልሜም በዉኔም የሚታየኝ ብቸኛ ቦታ በጽዶች እና በዝግባዎች የተከበበ ጸጥ ያለ ገዳም ነበር።

ይኼን ልጅ ካወቅሁት በኋላ፣ ሕልሜን በሌላ ሕልም አስለወጠኝ። እሸቴ
ይባላል።

እሸቴ!

ቆዳው ሞኛሞኝ፣ አእምሮው ግን እሳታማ የሆነለት ልጅ ነው። ወይ
ጭንቅላት! አወይ መታደል! ባልወደው ነበር የሚደንቀኝ። አነጋገሩ የጅል፣ ንግግሩ ግን የንጉሥ የሆነለት ልጅ ነዉ። እንኳን እሱ እናቱም ጭምር ለልብ የሚደርሱ የሙቀት ወንዛወንዝ ናቸው።

ጭልጥ አልሁለታ!

በዚሁ በሲራክ-፯ ጀማሪ አባል ሳለሁ፣ የመጀመሪያ ተልእኮ የተሰጠኝ የእሸቴ ጉዳይ ነበር፡፡ ከዚያ ቀደም ስሙን እና ዝናውን በሩቁ ከመስማት በቀር ትውውቁ አልነበረንም። ለመጀመሪያ ጊዜ በአካል ያየሁትም ያኔ የእሱን ጉዳይ ተልእኮዬ አድርጌ የተቀበልሁ ጊዜ ነው። በዚያን ጊዜ እሱ የአዲስ አበባ ኑሮ በአፍንጫዬ ይውጣ ብሎ፤ የት ይደርስበታል
የሚባልበትን የዩኒቨርስቲ ትምህርቱን እርግፍ አድርጎ ጥሎት አልዩ አምባ ወደምትባል ጥንታዊት ትንሽ ከተማ ከሸክላ ሠሪ እናቱ ጋር መኖር ጀምሯል፡፡ ሲራክ-፯ ደግሞ የእሸቴን የአእምሮ ያውቀዋልና፤ ይኼን የመሰለ ልጅ ባክኖ ከሚቀር ልጠቀምበት ብሎ ወሰነ።
የእኔ ተልእኮም እሱን ለሲራክ፯ አባልነት መመልመል እና ማብቃት
ነበር።
👍272😁1
ተልእኮዬን ገባሁበት። ግን፣ እንዳሰብሁት ቀላል አልሆነልኝም::
ለዚሁ ስል ብቻ በአልዩ አምባ ጤና ጣቢያ ጠቅላላ ሐኪም ሆኜ
ተቀጠርሁ። ለመቀራረብም ቢሆን እንኳን መጀመሪያ የግድ ከእሱ
መምጣት ስለ ነበረበት፣ እኔ በሽፋንነት የተዘጋጀልኝን የሕክምና ሥራ አንገቴን ደፍቼ መሥራት ጀመርሁ። ተልእኮዬ እንዲሰምርልኝ ከፈለግሁ፣
እሱን እንደምፈልገው ይቅርና ከነመፈጠሩ እንኳን የማውቀው መምሰል የለብኝም፡፡ በዚህም ምክንያት ከፊቴ መንገድ ዘግቶ ቢቆም እንኳን እንደማይታየው ነፋስ መቁጠር ጀመርሁ። ታዲያ፣ ከመንደሩ ከፍ ብሎ አንዲት ዓይኑግቡ ሥፍራ አለች። እሸቴ ሁልጊዜም ቢሆን ጀንበር ዘቅዘቅ
ስትል የእግር ሽርሽር ካደረገ በኋላ፣ በዚያች ጉብታ ላይ የማረፍ ልማድ እንዳለዉ ቀድሞዉንም ተልእኮዉን የሰጠኝ ሰዉ ገለጻ አድርጎልኛል። ስለሆነም ዕለት በዕለት ክራሬን ይዤ ከጉብታዋ ላይ የማልታጣ ሰዉ ሆንሁ። በእርግጥ ከጀንበሯ ጋርም ፊት ለፊት የምታገናኝ ቦታ ስለሆነች፣
ቦታዋ ለእኔም ድንቅ ናት። ሁልጊዜ እሄዳለሁ፣ ሁልጊዜ ያየኛል፣ ሁልጊዜ ያዳምጠኛል፣ ሁልጊዜም ማደናነቅ ጀምሯል።

በመሆኑም ዓይኑ ዉስጥ ለመግባት የፈራሁትን ያህል አልተቸገርሁም፡፡እንዲያውም ከሌሎቹ ወጣት ወንዶች ጋር
እየተደባበቀ እሱም
ሲያንዣብብኝ ቀናት አለፉ፡፡ ለሳምንታት እንዲሁ ቀጠልን። የኋላ ኋላ ማታ ማታ ጉብታዋ ላይ የሚያየኝ አልበቃ ብሎት አንዳንድ ቀን የታመመ ሰው እየደገፈ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ ራሱ ታማሚ እየመሰለ ወደ ምሠራበት
ጤና ጣቢያ መምጣት ጀመረ።

እንዲችዉ አመላለስሁት፡፡

“እእእእ እንዴት እንደሆነ እእእ እንጃ..” አለኝ አንድ ቀን፣ እንደ ልማዱ ራሴን ብሎ መጥቶ፡፡ ቀና አልሁለት፡፡ “መመመ መተዋወቅ አይቻልም?” አለኝ፣ ቀና ብዬ ማየቴን እንደ ምን እንደ ቆጠረው ሳይገባኝ። ‹አሁን ነው ጊዜው አልሁት ለልቤ። የክሊኒኩን በር መለስ አደረግሁት። ለነገሩ
የዘጋሁት እኔ ያለሁበትን ክፍል ነዉ። ግን ክሊኒኳ ያላት ክፍል አንድ ብቻ ስለሆነች፣ እሷም እኔ ያለሁባት ክፍል ስለሆነች፣ የኔን ክፍል ዘጋሁት ማለት ክሊኒኩን እንዳለ ጠረቀምሁት ማለት ነዉ። ይኼንን ሳደርግ ከየትና የት ድረስ እታከማለሁ ብሎ በፍዳ የመጣዉን ምስኪን ሕመምተኛ ሁሉ ማጉላላቴ አይቀርም፡፡ ባይሆን መልሼ ቶሎ መክፈት
ስላለብኝ፣ ያለ ተጨማሪ መግደርደር ለትዉዉቅ ፈቃደኛ የሆነ መልኬን አወጣሁለት።

“እእእ-እሸቴ እባላለሁ”

ቀጥል የማለት ያህል፣ ግንባሬን ፈታሁለት።

“ጓጓደ-ደደደደ-ኛ የየየ-የሚባል ሰ-ሰው የለኝም። ቀልጁ የሚስቅልኝ ሰው የለም፡፡ የ-የሚያዝንልኝም የለ። ለለለ-ለምን እንደሆነ ልልልል-
ልንገርሽ?”

እኔ እየቀጣጠልሁ እሰማዋለሁ እንጂ፣ አንድ ቃል ለማዉጣት ብቻ ዘመን ይፈጅበታል። ስለሱ ያን ያህል መረጃ ስሰበስብ፣ ስለ ተብታባነቱ ግን ማንም የነገረኝ የለም። ቢሆንም ግን ተብታባነቱ ሳይቀር የደስ ደስ አለዉ።
ያምርበታል። ቢያንስ እኔ ወድጄለታለሁ። ለመሸነፍ ይኼን ያህል በጫፍ ላይ ኖሪያለሁ እንዴ? ቀድሜ የሰማሁለት ዝናዉ ሳያዳክመኝ አልቀረም።የእሺታ ፊቴን አይቶ ቀጠለለኝ፣ እኔም እንደ ምንም እየቀጣጠልሁ
አዳመጥሁት።

“አአአ-አየሽ ብቸኝነት መቃብር ነው። ለብቻ መቅረት ሞት አይደለም? እኔ ዓይኔ ቢታወር እመርጣለሁ። ብቸኝነት ግን ከምንም የባሰ ገሀነም ነው። የፈለገ ቢሆን ከሰው እንዳለመላመድ መጥፎ ቅጣት ያለ አይመስለኝም። ጭንቁን አይጣልብሽ! ከሰው መሀል ሆኖ በሰው እንዳለመፈለግ ያለ ጭቆና የለም። ያማል! ያንገበግባል!”
ሊያለቅስ ደረሰ፡፡ አንጀቴን በላዉ፡፡

“እእእ እንዴት እንደሆነ እንጃ፤ አንድ ቀን ወደ ሴት ተራ መሄድ
አማረኝ። ብዙም አላሰብሁበትም ልበል? እኔ እንጃ። ብብብ ብቻ
መገኛቸዉን ከብዙ የአማርኛ መጻሕፍት ስላወቅሁ ፒያሳን መርጨ ወደዚያ ወጣሁ። ገበያ ታውቂያለሽ? ለዓይን ከያዘ ፒያሳን ብታያት ቁጭ ገበያ ናት። ያዉም ድብልቅልቅ ያለች የሴት ገበያ! ወንደኞችን ከሴተኞች
ታሽማምታለች። ከከከ ከላይ
እስከ ታች ሴተኞች ተጠጋግተዉ
ይሰለፋሉ። የጊዮርጊስ ገረገራውን ተደግፈው፣ የምኒልክ አደባባይን
ከበው፣ በሲኒማ ቤቶች ደጃፍ ተንቋጠው፣ የየሰቀላቸውን ጉበን
አንቀው፣ የሰሜን ማዘጋጃ መንገዱን ዘግተው ይቆማሉ። ወንደኛው ደግሞ እጁን በኪሱ ደብቆ እየገላመጠ በፊታቸው ያልፍልሻል። እኔም እንዲሁ ሁኔታውን እየታዘብሁ ወዲያ ወዲህ ስል፣ አንዷ አትጠራኝም
መሰለሽ? ‹እ ነፍሴ› አለችኛ! አፍሬ ስደነባበር መሬቱን ሳይቀር በእርግጫ ሳትሁት። አየር ላይ የምንሳፈፍ መሰለኝ። የሆነዉ ሆኖ ያልሰማሁ ለመምሰል ሞከርሁ። ዝዝ ዝም ብላ ተከተለችኝ”

ይኼን ሲል ሐፍረት ተሰማዉ። የባሰ አቀረቀረ፡፡ እኔ ደግሞ ገመናውን ከራሱ አፍ የመስማት ጉጉቴ የትና የት ደርሷል። እንዳያቋርጥብኝ ስለ ፈራሁ እንደ መወትወት ሁሉ ቃጣኝ፡፡

“እና? ተመለሺ አልካት?”

“እእእ እኔ?... እረ እኔስ ተመለሺም ተከተዪኝም አላልኋትም ነበር። እሷ ናት እንጂ፤ ጭጭጭጭጭ ጭራሽ ቀደመችኝ እና ወደ ሆነ መስቃላ ቤት ጎተተችኝ እንጂ። እዚህ ላይ ነዉ ታሪኬ የተለወጠዉ። ሌላ ዓለም ዉስጥ
ሌላ ነገር አየሁ። እንዲህ እንደ ዋዛ የገባሁበትን ሌላ ዓለም፣ በበነጋታዉም ደግሜ ማየት አሰኘኝ። እያደር እየለመድሁት መጣሁ። ጭራሽ ሱስ
ሆኖብኝ አረፈዉ። ከዚያ በኋላማ ምኑ ቅጡ! አጥር ተደግፋ የቆመች ሴት ሁሉ ገላ ሻጭ እየመሰለችኝ፣ ስንት ብር ነሽ? እላታለሁ ጠጋ ብዬ። ለብቻዋ ፈንጠር ብላ የቆመች ሴት ሁሉ አላልፍም። ወይ ውርደት!
ስስስስ ስንት ሰው አስደንግጫለሁ መሰለሽ”

እውነትም ገራሚ ልጅ አይደለም? ገና ስሙን ነግሮኝ እየተዋወቀኝ
ለመስለው ለእኔ ያለ ሐፍረት እንዲህ ከመሀሉ ጀምሮ መናዘዙ
አይገርምም? ቅሌቴ የሚለዉን ነገር የመናገሪያ አመጣዉ? እንዴት ሆነለት? በጣም ደነቀኝ፡፡ እኔ እሱን ብሆንስ?.....

ይቀጥላል
👍342👎1👏1
#ማወቅ_እና_ማመን

ከቀጠርኩሽ ቦታ ቀርተሻል አውቃለሁ
ያወቅሁትን እውነት
ማመን ቢቸግረኝ
ትመጣለች እያልሁ እጠብቅሻለሁ
“አትመጣም" እያለ
ለሚነግረኝ ሁሉ መቅረትሽን አውቆ
የቀረበት እንጂ
የመጣለትማ አያውቅም ጠብቆ
ብዬ እመልሳለሁ
በቃትመለሽ ቀርተሻል አውቃለሁ።

🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
👍238👏2😁1
#ገረገራ


#ክፍል_ሶስት


#በታደለ_አያሌው


..እውነትም ገራሚ ልጅ አይደለም? ገና ስሙን ነግሮኝ እየተዋወቀኝ ለመስለው ለእኔ ያለ ሐፍረት እንዲህ ከመሀሉ ጀምሮ መናዘዙ አይገርምም? ቅሌቴ የሚለዉን ነገር የመናገሪያ አመጣዉ? እንዴት ሆነለት? በጣም ደነቀኝ፡፡ እኔ እሱን ብሆንስ?አይደለም ለሌላ ሰው ልነግረው ይቅርና፣ ራሴንም እንደማልክደው እርግጠኛ አይደለሁም። እሸቴ የተለየ ሰዉ መሆኑን አመንሁ። ገራገር ነው። በዚያም ላይ በግልጽነቱ ላይ ወሰን አጣሁበት። ይኼን ሰው
ከማድነቅ በቀር አማራጭ የለኝም።

“ስለ ለምንድን ነው ግን የነገርሁሽ?” አለ፣ እንደ ማፈርም እንደ መሳቅም ብሎ።

“እንጃ” አልሁት፣ ባይነግረኝ እንደማለቅስ እያወቅሁት። በእኔ ቤት ለእሱ ግድ የሌለኝ መምሰሌ ነዉ። ዉሸት! ለምን ሆነና ስንትና ስንት ኪሎ ሜትሮች አቆራርጬ፣ እዚህ አልዩ አምባ የመጣሁት? ለእሱ ብዬ እኮ ነዉ። የገዛ ታሪኩን ከራሱ አፍ ለመስማት፡፡ ደካማ ጎኑን ለማወቅና የሲራክ ፯ አባል ለማድረግ ነዉ እዚህ ድረስ መምጫ ምክንያቴ፡፡ ቢሆንም
ግን እንደማዉቀዉ ሊያዉቅብኝ አይገባም፡፡ ስለዚህ የባሰ ፊት ነሳሁት።

“ቅቅቅቅቅቅ ቅሌታም ነኝ አይደል?”

“ነህ እንዴ?”

“ይኼን ያወቁ የግቢ ልጆች ምን ብለው ቅጽል ስም እንዳወጡልኝ
ታዉቂያለሽ?”

“ግቢ...?” አልሁት፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኮምፒዉተር ሳይንስ
ተማሪ እንደነበር ጠንቅቄ የማላውቅ ይመስል። እንኳንስ ይቺን፣ ስለሚያዘወትረዉ የካልሲ ቀለም ሳይቀር ተነግሮኛል። ግቢ ነበርህ እንዴ?” አልሁት አሁንም፣ ስለሱ ምንም እንደማላዉቅ መስየ።

“አዎ”

“እሺ፣ ምን አሉህ?”

“ዎዎዎዎ ዎከር”

“ዎከር?”

«ሂያጅ ማለታቸዉ እንደሆነ። ያያያያ ያው የቀላዋጭ መጠሪያው
እንደዚያ አይደል? እኔ ከዚያ በፊት ለማንም ሐሜት ደንታ የለኝም ባይ
ነበርሁ። ይኸኔ ግን ተሰማኝ። አመመኝ። በጣም አፈርሁ። ራሴን መናቅ ሁሉ ጀመርሁ። ተማሪ አስጠላኝ። አስተማሪ አስጠላኝ። ዩኒቨርስቲ አስጠላኝ። መማር ጠላሁ። በበበ በቃ ሁሉ ነገር ጉሮሮዬ ላይ መጣ።
የጀመርሁትን በጅምር ትቸው ወጣሁ። ከዚያ ሁሉም ነገር በአፍንጫዬ ይውጣ ብዬ ወደ እናቴ መጣሁ እልሻለሁ” አለና፣ ኧሁሁ ብሎ በረዥሙ ሲተነፍስ፣ ወዠቦ ያለፈ ነበር የመሰለኝ። ቅዝዝ ብዬ አየሁት፡፡ አዘንሁለት። ሰነባብቼ እንዲያዉም ሲራክ፤ ከሰጠኝ ተልእኮዬ ጎን ለጎን
ለእሱ ማዘኑንም ለራሴ እየደረብሁበት መጣሁ፡፡ ይባስ ብዬ ራሴን ሳታልለው ደግሞ «እሸቴ እኮ የእኔ እርዳታ ያስፈልገዋል ማለት ጀመርሁ። አዝኜ ሞትኋ! እኔ ማነኝና ለእሽቴ አዝናለሁ? ዉሽት።
የምንኩስና ምኞቴን የሚያስረሳ ቦታ በልቤ ዉስጥ ጠርጌ ማስረከቤን ላለማመን የፈጠርኋት መሸንገያዬ ናት። መከጀሌን ከውርደት ብቆጥረው
እንጂ አሸንፎኛል። በቃ ገዳም የሚለዉ የልጅነት ምኞቴ ቀረና ትዳር ያሰኘኝ ጀመር። መነኩሴነት ቀረ እና ሚስትነት በዓይን በዓይኔ ዞረ። በእርግጥ እሱ ብቻ ሳይሆን እኔም አሸንፌዋለሁ። ማኅበሩን ጨምሮ ጠላሁት ያለውን ነገር ሁሉ አስወድጀዋለሁ። ልክ እንደ ተላክሁት ሄጄ አምጥቼዋለሁ። ማምጣት ብቻ ሳይሆን የሲራክ-፯ አባል ማድረግ ችያለሁ። ያዉም ተራ ሳይሆን፣ እንደ ዓይን የሚቆጠር መኩሪያ አባል።

ተልእኮዬን በፍጽምና ተወጥቼዋለሁ።

ከዚያ በኋላ አፍ አዉጥተን ፍቅረኛሞች ነን ባንባባልም፣ ያዉ ሆነናል። በበኩሌ ልቤን ሰጥቼዋለሁ፡፡ ስለ እሱ ሞኝነት እና ጉብዝና መስማቱ ሱስ ሆኖብኛል፡፡ እሱም ቢሆን አይቶኝ እና እንጉርጉሮዬን ሰምቶ አይጠግብም፡፡ነገር ግን ገና ማንም ያወቀብን አይመስለኝም፡፡ ምናልባት፣ ባልቻ እና
የእሽቴ እናት ጥርጣሬው ይኖራቸው ይሆናል እንዳይታወቅብን የተለየ ጥንቃቄ አድርገን ሳይሆን እኔ ክራሬን ይዤ
ወደ አደባባይ ስወጣ ብዙ ወጣት ግልብጥ ብሎ እንደሚያጅበኝ የታወቀ በመሆኑ ይመስለኛል
በሲራክ ፯ ማዕከልም ቢሆን ከብዙዎች ጋር ጥሩ ቀረቤታ ስላለን፣ የእሽቱን የተለየ አያስመስለውም። ወይ
እኔን በእንዲህ ያለ ነገር
የሚጠረጥረኝ አይኖር ይሆናል፡፡ በተለይ ቤተሰቦቼ ሴትና ወንድ እንኳ ለይቼ ማወቅ የሚሆንልኝ አይመስላቸዉም፡፡ እንዲያውም አንደኛዋ እህቴን ልነግራት ስሞክር፤ አንቺ እንኳን እንደ እሸቴ ላለ ዘሟች ይቅርና ለጳጳስ ልጅም አትደነግጭት ብላኛለች፡፡ ጳጳስ ልጅ እንደማይወልድ ጠፍቷት ሳይሆን ምን ያህል እኔን በእንዲህ ዓይነት መንገድ
እንደማትገምተኝ ስታሳምነኝ ነው።

አላወቀችኝማ፣ ለእሽቴ ስል የማይተወዉን ሕልሜን እንደ ተዉሁት።

“እኔ ምልህ እሸቴ” አልሁት፣ በዚያች ጎደሎ ምሽት በእኔ ቤት እራት በልተን ከመጨረሳችን። ቀደም ብሎ፣ አመሻሹ ላይ ከጀንበሯ ፊት ክራር ይዤ ሳለሁ፣ እኔን ከብቦ እንጉርጉሮዬን በስስት የሚያዳምጠኝን ሰዉ
ሁሉ ከምንም ሳልቆጥር ረግጬ፤ እሱን ተከትዬዉ ቀጥታ ወደኔ ቤት
ነበር እራት እንብላ ብዬ የወሰድሁት።

“ትናንት” አልሁት፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ወይን ለመቅመስ እጄን ወደ
ብርጭቆዉ እየሰደድሁ። አልኮል የሚባል ነገር በአፌ ዞሮ ስለማያውቅ፣ ምን ምን እንደሚል መቅመሱ ሳያጓጓኝ አልቀረም።

“ትትትትት-ትናንት ምን?”

አንድ ነገር ብጠይቅህ ሳትደብቅ ትነግረኛለህ እ?”

“ካካካ ካንቺ መደበቁ ሆኖልኝ እኔ?”

“አዉቃለሁ፣ አትደብቀኝም”

“ስስስ-ስለኔ ላንቺ ምንድነዉ ያልነገርሁሽ ዉቤዋ?”

“ትናንትና በዚህ ሰዓት የት ነበርህ?” አልሁት ዓይን ዓይኑን እያየሁ፣ ቁርጥ አድርጌ፡፡

“ትትትት ትናንትና?” አለ፣ ደም እንደሚጎነጭ ዝግንን ብሎት የወይኑን ብርጭቆ ወደ አፉ እያስጠጋ።

“የት ነበርህ?”

እንደ ትኩስ ቡና በፍራቻ ፉት ያለዉን ወይን በአፉ እንደ ያዘዉ ለረዥም ጊዜ ጣሪያ ጣሪያዉን አየ። እኔም ልቤ ለምላሹ እንደ ተንጠለጠለች፣ በዝምታ ጠበቅሁት። የጠረጠርሁት ነገር አለ። መቼም ዐመል በዋዛ
አይለቅምና፣ ምናልባት ወደ ሴተኛ አዳሪዎች መሄዱን የተወዉ
አልመስልሽ ስላለኝ ነዉ አጠያየቄ፡፡ ቢሆንም፣ ከእሱ ጋር ያለዉን እዉነት መስማት አለብኝ፡፡ እኔን እንደማይዋሸኝ ደግሞ አዉቃለሁ። እንኳንስ እንዲህ እየተቁለጨለጭሁ ጠይቄው ይቅርና፣ ድሮዉንም ግልጽነቱን
ማንም እንደ እሱ አልታደለዉ። የት ነበርሁ ይለኝ ይሆን?

“እእእ አልሆነልኝማ” ብሎኝ አረፈዉ፣ እንባ በዓይኑ ጢም እያለበት፡፡
እንደ ፈራሁት!

“ምን ማለት ነዉ አልሆነልኝም ማለት?”

“በቃ ሄጄ ነበር። እሱን አይደል የምትጠይቂኝ? ትናንትና በዚህ ሠዐት ፒያሳ ዶሮ ማነቂያ ነበርሁ”

“እኮ ምን ልትሆን!?”

“አአአ አልቻልሁም። ምን ጎትቶ እንደሚወስደኝም አላውቀው። ምኑ ሽዉ እንደሚያደርገኝ ሁሉ እንጃለቴን። ግን ትናንትም ሴተኛ አዳሪዎች ጋ ሄጄ ነበር። አቅቶኛል እኔ”

እየየ ብለን ተላቀስን። እንባዬ እየወረደም ንዴት ተናንቆኛል። እየቆየማ ጥርሴ ሁሉ ተፋጨብኝ። ይኸኔ በንክሻ ብዘለዝለዉ ሁሉ የልቤ አይደርስም። ለንዴቴ ማብረጃ አጣሁለት።

“ደግሞ አታፍርም? ጀብዱ እንደ ፈጸመ ሰዉ ጉድህን ስትናገር ሐፍረት የሚባል የለህም!?”

“ብዋሽሽ የባሰ አታዝኝብኝም ነበር?”

“ዋሽተህ መሞከር ነበራ! ሁልጊዜ አንድ ዓይነት መልስ አያሳፍርህም? ሁልጊዜ ‹አቃተኝ ስትለኝ አታፍርም!? ጨክነዉ ከተዉት እንኳን ዝሙት
ሌላዉስ ይቀር የለም እንዴ!?
ሁልጊዜ አንጀቴን የምትበላው
ይመስልሃል? ቆይ ጅል ነዉ እንዴ የምመስልህ!?”

ሌላ መልስ አጣ። ደግሞ ምናባቱንስ ይመልስልኛል?

“ልንገርህ አይደል? አንተ መቼም አያልፍልህም! መቼም አትለወጥም!”

“አሳፈርሁሽ አይደል?”

“ነገርሁህ። ተንፏቀህ ተልከስክሰህ ትቀራታለህ እንጂ፣ መቼም
አትለወጥም!”
👍432
“እእእ .እእ..እባክሽ አግዥኝ። አንቺ አግዘሽኝ ያልሆነልኝ ነገር የለም።
በማርያም እርጅኝ”

“ባክህ ወደዛ! የራስህ ጉዳይ!!” ብየ አበሻቀጥሁት፣ የበለጠ ብልጭ ብሎብኝ። ልቤ የሚረጨዉ ደም ያለ ቅጥ እንደ ፈላ ይታወቀኛል።
ዉስጤን ለመጠጠኝ። ለወትሮዉ እንኳንስ እንደዚህ የሰማዩንና የባሕሩን ኗሪዎች ጨምሮ እስከማስደንገጥ ይቅርና፣ ማንንም ኃይለ ቃል ተናግሬ
አላዉቅም። ልክ እንደ ወይኑ መጠጥ ሁሉ፣ እንዲህ ስቆጣም
የመጀመሪያዬ ይመስለኛል። እንደ ነባር ጠጭ ብርጭቆዬን ብድግ አድርጌ ወይኑን ባንድ ትንፋሽ ጨለጥሁት። ፊልም ላይ እንዳየሁት መጠጡ
ጉሮሮዬን ፍቆኝ ዓይኔን ያስጨፍነኛል ብዬ ስጠብቅ፣ እንዲያዉም ጥፍጥናዉ ነዉ አፌ ላይ የቀረብኝ። ጠጪኝ ጠጪኝ፣ ድገሚኝ ድገሚኝ አለኝ፡፡ ድጋሚ ጢም አድርጌ በብርጭቆዉ ቀዳሁበትና አሁንም ልምድ
እንዳለዉ ጠጪ ግርግጭ እያደረግሁ በጉሮሮዬ አንቆረቆርሁት። ወይኑ
ወደ ጉሮሮዬ በወረደ ቁጥር ስካር ወደ ጭንቅላቴ፣ የተንቀለቀለ ቂም
ደግሞ ወደ ልቤ ሰተት ብሎ ሲገሰግስ ይታወቀኛል። ያባብለኛል ብዬ የጠበቅሁት እሸቴ፣ ገና ለገና የራስህ ጉዳይ ስላልሁት ሐሞቱ ፈሷል።እንዲያዉም አልቅስ አልቅስ ብሎታል፣ እንኳንስ እኔ ፊት ነስቼዉ። እኔ ደግሞ ምን ስል ነዉ ይህን ሰዉ ሕልሜ ያደረገሁት ስል ራሴን አጠቃሁት፡፡ ንዴት ቀላቅሎ፣ ቁጭት መታኝ፡፡ ወይኑን ከነጠርሙሱ አንስቶ መጨለጥ አሰኘኝ፡፡ የጠርሙሱን አንገት አፈፍ አድርጌ አነሳሁትና
አንዶቀዶቅሁት።

“እንዲህ ነኝና ልጅቷ!” ስል ተገለገልሁ፣ ግማሽ በግማሽ የስካር ሐይቅ ዉስጥ ገብቼ፡፡ እሸቴ በብርጭቆዉ ጠብ ያደረገዉ እና በጉንጩ የያዘዉ
ሲቀር፣ አንድ ሙሉ ጠርሙስ ብቻዬን ፈጀሁ ማለት ነው። “ወይን
እንዲህ ጣፈጭ ኖሯል ለካ!” ስል እንደ ጥንባዣም ተለፋደድሁ።

“ሰሰሰ ሰከርሽ እንዴ ?”

“ሰከርሁ እንዴ?”

“እረ አፍሽ እየተሳሰረ ነዉ ዉቤ”

“ምናገባህ! እሰይ እንኳን ሰከርሁ!”

“ስካርስ አያምርብሽም”

“ሂድ ሂድሂሂድድድድ...”

ትክትክ ብዬ ሳቅሁበት። ሳቄን ተቀብሎ እሱም አሽካካብኝ። ሳቁ
ለመጀመሪያ ጊዜ አስጠላኝ፡፡ የሆነ የጉርጥ መንጋ መሀል ያለሁ መሰለኝ፡፡
ድምፁ ሰቀጠጠኝ። ጠላሁት።

ሆሆሽ. በይ ልሂድልሽ። አንቺም ብትተኝ ይሻልሻል” ብሎ
ከመቀመጫዉ ሲነሳ፣ በብዥታ ይታየኛል። እንደገና እንባዬ እስኪወርድ ሳቅሁበት።

“ወደ ሴተኞቹ መሄድህ ነው እ?” አልሁት፣ ሳቄ እንደ ሳል እያካለበኝ።
“ጅል! ይልቅ ቅድም እርጅኝ ብለኸኝ አልነበር? ና ተቀመጥ ልርዳህ”

“እአአ አይ ነገ...”

“አሁንስ? አሃ... ሰዓት አሳለፍሁብህ መሰለኝ። ለመሆኑ የት ሰፈር ያለችዋ ናት የዛሬዋ ተረኛ? ሰባተኛ ነዉ እ? ወይስ የጨርቆሷ? መቸስ ጭፈራ ቤት የሚቆሙት ላይ ገና አልደረስህም። አይደል? ወይስ ደርሰሃል? አይዞህ አይዞህ በዚህ አያያዝህ ከዋናዎቹ የገላ ደላላዎች ጋር መተዋወቅህ ስለማይቀር፣ የምትፈልጋትን ዓይነት ሴት እቤትህ ድረስ
ያስመጡልሃል። ሃሃሃ... ይልቅ አንተ ደከመኝ ሰለቸኝ አትበል። ለነገሩ እነዚህ በየጉራንጉሩ ያሉትስ ማን አላቸዉ? ማዳረስ እኮ ይጠበቅብሃል።

መቼስ ጎዳናዉ ሁሉ በአዳሪ ሴቶች አይደል የተጥለቀለቀዉ?... ደግሞም እኮ ከመንገድ መብራቶች ይልቅ፣ መንገድ ዳር የሚቆሙ ሴተኞች
እንደሚበልጡ ነግረኸኛል። እኔ ራሴ ትናንትና ከቤተ መንግሥት በር ላይ የቆሙ ሴተኞች በዓይኔ በብረቱ አይቼ ገርሞኝ ልሞት። በቤተ መንግሥትም ዉስጥ ቤርጎ አለ ማለት ነዉ? ዞሮ ዞሮ አይዞህ በርታ። አላስመሸሁብህም አይደል? ትደርሳለህ ግን?”

በኃይል አሽካካሁበት፡፡

“እረ በእናትሽ፤ በእናትሽ ተይ”

“እሁ!” አልሁ፣ ያለሁበት እየተንጨዋለለብኝ፡፡ ዓለም በዙሪያዬ ስትሽከረከር ይታወቀኛል። ወደ ሌላ ዓለም እንደ ገባሁም ጠርጥሬያለሁ።
ከዚያ በኋላ የሆነዉን የቱንም አላስታዉሰም፡፡ ብቻ ግን በነጋታዉ
አረፋፍጄ ከእንቅልፌ ስባንን፣ ራሴን በራሴዉ አልጋ ዉስጥ ነዉ
ያገኘሁት። ትልቅ የድንጋይ ወፍጮ ራሴ ላይ የተጫነብኝ ያህል ናላዬን
ክብድብድ ብሎኛል። ጭንቅላቴን በኹለት እጄ ጨብጬ እንደ ምንም ለመነቃቃት ሳዛጋ፣ አንድ የሚንሰቀሰቅ ድምፅ ከአጠገቤ ተሰማኝ። ቀና ብዬ ሳየዉ እሸቴ እያለቀሰ ነዉ።

“ምነዉ አንተ?” አልሁት፣ ገስግሶ በጠዋቱ ወደ ቤቴ እንደ መጣ
በመገመት፡፡ ከብርድ ልብሴ በሥር ገላዬን ስዳብሰዉ ምንም የቀረ ነገር የለም። የጡት ማስያዣዬ ሳይቀር፣ ሁሉም ልብስ ወላልቋል። መቼ እንዳወለቅሁት ሁሉ ትዝ አይለኝም። እሸቴን አየሁት፣ አሁንም ያለቅሳል።

“ምን ሆነሀል? ምነዉ እናትህ ደህና አይደሉም?”

እየባሰበት መጣ። ንፍጥ እና ለሃጩ እስኪዝረከረክ ድረስ እህህ አለ። ለማባበል ከነብርድ ልብሴ ወደ እሱ ስንፏቀቅ ይሸሸኛል። በራሱ ጊዜ ዝም ለማለት ሲሞክር ደግሞ ሲቃ ያካልበዋል፡፡

“እናትህን ምን አገኛቸዉ?”
“ምምም-ም-ምንም አልሆነች እእእ-እሷ”

“እና ምንድነዉ?”

“ገደልሁሽ እኮ ዉቤ”

አሁንም ይንሰቀሰቃል፡፡ እኔን ግን እንደ መሳቅም ገፋፋኝ፡፡ ገና ሳቁን
ሳልጀምረዉ ግን አንድ ነገር ዓይኔ ዉስጥ ጥልቅ አለ። በቦታዉ ላይ
ያጣሁትን የዉስጥ ሱሪዬን በእሸቴ እግሮች መካከል ወድቆ አየሁት::
ቅፍፍ አለኝ፡፡ ጭዉ አለብኝ፡፡ እንዳልዉጠውም እንዳልተፋዉም አጉል ሆኖ፣ ምራቄ ጉሮሮዬ ላይ ቀረ። የገዛ ምራቄ በትንታ አንፈራፈረኝ፡፡ ትንፋሽ አጠረኝ፡፡

“ገገገ ገድየሻለሁ” አለ፣ እንደገና እንባዉን እያዘነበዉ።
እሱ ባይሆንም ገዳዩ፣ መሞቱንማ ከዚህ በላይ? ሞቻለሁ እንጂ፡፡ የአባቴ ነፍስ ለምንኩስና እንደ ተመኘችኝ፣ እናቴ ደግሞ ለተክሊል እንደ ጠበቀችኝ ቀረሁ። ለእናቴም ለአባቴም ምኞት ሳልበቃ ቀረሁ። ጓደኞቼም፣ እህቶቼም፣ ወንድሞቼም እንደ ኮሩብኝ ሳልሆን ቀረሁ። የገዛ ዕድሌን
አልከሰከስሁት። በቃ በአንድ አዳር ዕድሜ ምንም ሆንሁኝ። ከዚህ በኋላ ምንድነኝ እኔ? መደዳዉን ለቀናት ብተኛም አልሻልሽ አለኝ ልክ እንደ ጽኑ በሽተኛ፣ ከወደቅሁበት መነሳት አቃተኝ።

መሞቴን አምኜ ተቀበልሁ።

እሸቴ ለቀናት አባብሎ አባብሎ ሲያቅተዉ በስንተኛዉ ቀን እንደሆነ እንጃ፣ የሆነ ምሽት ላይ እናቱን ይዞ መጥቶ ደግሞ ሞከረኝ። ትከሻዬን መታ
መታ አድርገዉ ከሞትሁበት ቀሰቀሱኝ። ለወትሮዉ እናቱን የታቦት ያህል አከብራቸዉ ነበር። አሁን ግን እሳቸዉ መሆናቸዉን ሳይ የባዕ ተቅበዘበዝሁ። እግዚአብሔር ራሱ ዘንበል ብሎ እንደሚያናግረኝ አፍሬ
መሸሸጊያዉ ጨነቀኝ፡፡ ብርድ ልብስ ዉስጥ ከነሙሉ ልብሴ የወደቅሁ ቢሆንም፣ መለመላዬን ያጣሁ ያህል ነዉ የሚሰማኝ፡፡ ክብሬ ተገፏል። ርቃኔ ቀርቷል።

እሳቸዉ እንደ ነገሩ አጽናኑኝ፡፡ተቆጥተዉኝም፣ መክረዉኝም፣
አባብለዉኝም፣ ሄዱ።

ሆኖም ራሴን ወደ ቀድሞዋ ዉብርስት መመለስ አልሆነልኝም፡፡ እሸቴን
ይቅርና ራሴን ይቅር የማልል፣ ራሴን የማልወድ ሴት ሆኜ አረፍሁት።እሸቴማ ከፈለገ ዛሬዉኑ ድፍት ቢል መቃብሩ ላይ እንኳን መድረስ አልፈልግም።

የጉድም ጉድ ሲያመጣብኝ ደግሞ፣ የወር አበባዬን ብጠብቀዉ ብጠብቀዉ
ጠልቆ ቀረ። አጅሬ ለካ በሆዴ ቀርቷል። ተጋለጥሁ። እንግዲህ እንዲሁ በድንገት የልጅ እናት መሆኔ ነዋ! ይኼስ እንዴት ተብሎ ለማን ይነገራል? እንዳይታወቅብኝ የማላደርገዉ ጥረት አልነበረም። ያለወትሮዬ ወፍራም
👍191👎1
ባለ ዘርፍ ሹራብ መደረብ አዘዉትሬያለሁ። ከሰዉ ጋር ስቆም፣ ሆዴን ሰልቤ ወደ ፊት ዘመም እላለሁ። ቢሆንስ ግን ሽል አይደል ነገርዮዉ? እስከ መቼ መደበቅ እችል ኖሯል? እንኳንስ በልብስ በምንም መደበቅ
እንዳልችል አድርጎ እየፈጠጠ መጣብኛ! በእኔ ቤት ማንም አላወቀብኝ ብዬ ከራሴ ጋር ስሹለከሎክ፣ ይኸዉ ቢያንስ እናቴ እና የማኅበሩ ሊቀ መንበር አዉቀዉብኛል። ሌላዉም ሳይነግረኝ እየተጠቋቆመብኝ ነዉ
እንጂ፣ ይኸኔ ጉዴ ገሀድ ወጥቶብኛል በቃ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የሚከፈት የበር ድምፅ ሰምቼ ቀና ስል፣ ጠዋት ከእመዋ ጋር ተሰነባብቼ ከበዓታ ገዳም ስወጣ ‹እህቱ አይደለችም ብለዉ ለዉርርድ የደረሱበት ወንድሜ ጃሪም የሸሚዙን እጅጌ ሰብስቦ ከፊቴ ቆሟል።

“ጭራሽ!” አለ፣ የወትሮዉ ፊቱ ልዉጥዉጥ እንዳለ።.....

ይቀጥላል
👍134😁1🤔1
#ምንዱባን


#ክፍል_አርባ_አምስት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

...«ዣቬር ይህ ሁሉ ሲሆን ድምፅ አላሰማም፡፡ ከቋሚ ብረት ጋር
በመታሠሩ መነቃነቅ አይችልም፡፡ እነኩርፌይራክና ኮምብፌሬ ተመለከቱት።
«ሰላይ ነው» ሲል ኢንጆልራስ ኋላ ለመጡት ጓደኞቹ አስረዳቸው::
ወደ ዣቬር ዞር ብሉ «ምሽጋችን ከተያዘ ትገደላለህ» አለው::
«ለምን አሁኑኑ አትጨርሱኝም» ሲል ቁጣ በተሞላበት እንደበት
ዣቬር ጠየቃቸው::
«ጥይት እንዳይባክን» ሲሉ መለሱለት::
«ለምን በቢላዋ አንገቴን አትቆርጡትም፡፡»
«አንተ ሰላይ» አለ መልኩመልካሙ ኢንጆልራስ፡፡ «እኛ ዳኞች ነን እንጂ ቅጥር ነፍሰ ገዳዮች አይደለንም፡፡»
ከዚያም ጋቭሮችን ጠራው፡፡
«አንቺ፣ ሂጅና የተላክሽበትን ፈጽሚ፡፡ የነገርኩርህን ፈጽመህ በቶሎ ተመለስ፡፡»
«መሄዱ ነው» ብሎ ጮክ ብሎ ተናገረ፡፡

ሊወጣ ሲል መለስ ብሎ «በነገራችን ላይ የሰውዬውን ጠብመንጃ ለእኔ አትሰጡኝም?» ሲል ጠየቀ፡፡ «ሙዚቀኛው ለእናንተ፣ ዋሽንቱ ግን
ለእኔ ቢሆን መልካም ነው፡፡)

ሁሉም ሳቅ አሉ ከዣቬር በስተቀር፡

ጋቭሮች ወጥቶ እንደሄደ የሆነውን አሳዛኝ ታሪክ ባይነገር ሕዝባዊ
እንቅስቃሴ በሚካሄድበት ጊዜ ምን ዓይነት ድርጊት እንደሚፈጸም አንባቢ ሊያውቅ አይችልም፡፡ ቢያውቅም እውቀቱ የተሟላ አይሆንም፡፡

ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በበረዶ ሊመሰል ይችላል፡፡ አንድ ዓይነት
እንቅስቃሴ በሚነሳበት ጊዜ ሕዝብ ከየት መጣ ሳይባል እንደ ክረምት በረዶ ይቆለላል፤ ይሰበሰባል፡፡ ሰዎቹ ከየት እንደመጡ አይጠያየቁም። ዝም
ብለው ይሰበሰባሉ፡፡ በዚህ ዓይነት ከተሰበሰቡት ሰዎች መካከል ከየት እንደመጣ የማይታወቅ አንድ ወዝ አደር ነበር፡፡ የለበሰው ጃኬት ከክርኑ ላይ ተቀድዷል፡፡ አጢነው ሲመለከቱት የሰካራም መልክ ነው ያለው፡፡ ይህ
ሰው አብሮአቸው ከቆሙት ሌሎች ሰዎች መካከል የሚያውቀው የለም፡፡ ከዚያ እንደቆመ ሲናገር እንደ ሰካራም ወይም ሳይሰክር አውቆ የሰከረ ለመምሰል እንደሚንተባተብ ሰው ይንተባተባል፡፡ በድንገት ወደ ዋናው አውራ ጎዳና እያየ በሰካራም አንደበት ይናገራል::

«ጓደኞች፣ ታውቃላችሁ? የመጀመሪያውን ተኩስ የምንከፍተው ከዚያች
ማዶ ከምትታይ ቤት ውስጥ ሆነን መሆን አለበት:: የመስኮቱን ጥግ ይዘን ከተኮስን በማንም አንበገርም::»

« ቤቱን እንዲከፍቱ ማንኳኳት ነዋ!»

«ቢንኳኳም አይከፍቱም::»

«እኔ አስከፍተዋለሁ» በማለት ያ ሰው ራሱ ወደ ጠቆመው ቤት
አቅጣጫ አመራ:: ከበሩ ላይ ሆኖ አንኳኳ፡፡ ቤቱ አልተከፈተም። ደግሞ በኃይል አንኳኳ፡፡ ጥቂት ቆይቶ ለሦስተኛ ጊዜ በድፍረት በኃይል አንኳኳ፡፡ አሁንም ዝምታ ሆነ፡፡

«ቤቶች! እዚህ ቤት! ሰው የለም እንዴ?» ሲል በጣም ጮክ ብሎ
ተናገረ:: የሚንኳኳ ድምፅ ወይም የሚንቀሳቀስ ፍጡር አልነበረም:: በያዘው ጠብመንጃ ሰደፍ በሩን በኃይል ቀጠቀጠው:: ከድብደባው ብዛት ቤቱ የተነቃነቀ
መሰለ፡፡ ይህ ሲሆን ከመስኮቶቹ አንደኛው በጥቂቱ ተከፈተ:: ከውስጥ የሻማ ብርሃን ታየ:: ፀጉራቸው የሸበተ ሽማግሌ ሰው አንገታቸውን ብቅ አደረጉ።

በር ደብዳቢው መደብደቡን አቆመ::

“ምን ይፈልጋሉ ጌቶች?»

«በሩን ክፈትልን» ሲል መለሰላቸው::

«ጌታዬ ፣ ይህ ሊሆን አይችልም::

«ክፈት ብያለሁ፤ በሩ ቢከፈት ይሻላል::»

«አልችልም ጌታው::»

ጨለማ ስለነበር መሣሪያውን ሲያነጣጥርባቸው አላዩትም::

«እሺ ወይስ እምቢ?
አትከፍትም?» ሲል እንደገና የቤቱን ጌታ ጠየቃቸው

«እምቢ፣ አልከፍትም» ሲሉ መለሰሉት::

«እምቢ አልክ?»

«አዎን የእኔ ጀግ…»

የሚሰጡትን መልስ ሳይጨርሱ ጠብመንጃው ተተኩሶ ግንባራቸውን ተረተረው:: ጥይቱ ከፊት ገብቶ ከኋላ በኩል ወጣ፡፡ ሰውዬው ጩኸት ሳያሰሙ መስኮቱ ላይ ተደፉ፡፡ ደማቸው ከመሬት ላይ ተንጠባጠበ:: ከመስኮቱ ላይ ሲወድቁ ሻማውን ነክተውት ኖሮ ከወለል ላይ ወድቆ መብራቱ ስለጠፋ ቤቱን ጨለማ ወረረው::

«ወንዱ» ሲል ገዳዩ ፎከረ፡፡ የጠመንጃውን አፈሙዝ ወደ መሬት እየመለሰ፡፡ ይህን ቃል ከአፉ አውጥቶ ሳይጨርስ አንድ ሰው ከኋላው መጥቶ ትከሻውን ጨምድዶ ያዘው::

«እጅ ወደ ላይ!» አለው::

ገዳዩ ፊቱን ቢያዞር ኢንጀልራስ እንደሆነ አወቀ፡፡ ጣቱን ከያዘው
ሽጉጥ ላይ አሳርፎአል:: የጠመንጃው ድምፅ ሰምቶ ነው ሲሮጥ የመጣው። ግስላ መስሎአል፡፡

«እጅ ወደ ላይ!» ሲል በድጋሚ ተናገረ፡፡

የሃያ ዓመቱ ወጣት በድንጋጤ እጁን ወደ ላይ ከዘረጋ በኋላ ከጭቃ ላይ ተንበረከከ፡ በአንድ ጊዜ ፊቱ ቀላ:: ሲደነግጡ የፈረንጅ ገላ መቅላት
የተለመደ ነው፡፡ ከዚያ የተሰበሰበው ሰው ዓይን ሁሉ ከእርሱ ላይ አረፈ፡፡
ሰው ሁሉ ዝም አለ፡፡ ገዳዩም ለመከላከል ወይም ለመናገር አልደፈረም።

ኢንጆልራስ ትከሻውን ለቅቆ ከመሬቱ ላይ በግንባሩ ደፋው፡፡

«አሳብህን ሰብስብ» አለው:: «ጸሉት ማድረስ ከፈለግህ መጸለይ ትችላለህ፡፡ ሌላም የምታስበው ነገር ካለ አስብ፡፡ ያለህ ጊዜ አንድ ደቂቃ ብቻ
ነው፡፡»

ማረኝ ይቅርታ አድርግልኝ፤ ተሳስቼአለሁ» ሲል ተንተባተበ፡፡
ከዚያም እንጀልሪስ እግር ላይ ተደፋ::

ኢንጂልራስ ዓይኑን ከወጣቱ ዓይን ላይ አላነሳም፡፡ ለአንድ ደቂቃ ጊዜ
ጠበቀው:: አንድ ደቂቃ ሲሞላ ከእግሩ ስር ይንደፋደፍ የነበረውን ሰው ፀጉር ይዞ ከጎተተው በኋላ እንደገና ወደ መሬት ወረወረው:: የያዘውን ሽጉጥ ቃታ ሳብ በማድረግ ጆሮው ላይ ለቀቀበት፡፡ ከዚያ የነበሩ ሰዎች ሁሉ
ወደመሬት አቀረቀሩ፡፡ ሟቹ ከጭቃው ላይ ተደፋ፡፡ ኢንጆልራስ ለመሞት የሚያጣጥረውን ሰው በእግሩ ከገፈተረ በኋላ የሚክተለውን ተናገረ፡፡

«ይህን ጥምብ ከምሽግ ውጭ ወርውሩና ጣሉት::»

ሶስት ሰዎች የሚያጣጥረውን ወጣት ከመሬት አንስተው ከምሽጉ ውጭ አውራ ጎዳና ላይ ወርውረው ጣሉት::

ኢንጆልራስ በአሳብ ተመስጦ ጥቂት ከቆየ በኋላ ከአሳቡ ይነቃል፡፡ራሱን ሰብሰብ አድርጎ ጸጥታውን በንግግር አደፈረሰ፡፡

«ጓዶች›› አለ ኢንጀልራስ፧ «ይህ ሰው የፈጸመው ተግባር አስጸያፊ
ሲሆን እኔ የወሰድኩበት እርምጃ ደግሞ አስከፊ ነው:: የሰው ሕይወት ስላጠፋ ነው የገደልኩት:: ይህን ቅጣት የፈጸምኩት ተገድጄ እንጂ ወድጄ
አይደለም:: እንቅስቃሴያችን ሥርዓት እንዲኖረው ያስፈልጋል:: የሰውን ሕይወት ማጥፋት ታላቅ ወንጀል ነው:: የአብዮታችን ዓይን እንደሚያየን መርሳት የለብንም:: እኛ የሪፑብሊክ ቄሶች ነን:: ኃላፊነት ስላለብን ፍልሚያችን በማንም መታወክ የለበትም:: በዚህ ምክንያት ነው ይህ ሰው
የፍርድ ውሳኔ የተበየነበትና አስፈላጊወም እርምጃ የተወሰደበት:: ፍርዱን የበየንኩት በዚህ ሰው ብቻ ላይ ሳይሆን በራሴም ላይ የፈረድኩ ስለሆነ
ውጤቱን ወደፊት የምታዩት ይሆናል::

የመጨረሻውን አነጋገር የሰሙ ሁሉ ተሸበሩ፡፡

«በአንተ ላይ የሚደርሰውን ሁሉ እኩል እንካፈላለን» ሲል ኮምብፌራ በጩኸት ተናገረ::

«ይሁና» ሲል ኢንጀልራስ መለሰለት:: «አንድ ነገር አለ ደግሞ:: የዚህን ሰው ብያኔ በማስፈጸም የሚጠበቅብኝን ግዴታ ነው የተወጣሁት::»
የወጣቱ ነፍስ ከወጣች በኋላ ልብሱ ሲመረመር ከኪሱ ውስጥ የፖሊስ አዛዥ ካርድ ተገኘ፡፡ ይህ ሰው ቆይቶ እንደተደረሰበት ከማሪየስ ቤት መጥቶ ማሪየስ የት እንዳለ ኩርፌይራን የጠየቀው ወጣት እንደሆነ ታውቋል፡፡

ማሪየስ ከጥላው ሥር ተደበቀ
👍9
በጠፍ ጨረቃ ከኮዜት አጥር ግቢ ውስጥ ኮዚትን ሲጠብቅ በስሙ
የጠራው ድምፅ የሕይወቱን ፍጻሜ ይዞለት የመጣ መሰለው:: «አሁንስ የእድሜዬ መጨረሻ በሆነ» ሲል ተመኘ:: ያ በጨለማ በስሙ የጠራው ድምፅ የመቃብር ቤት የሚያንኳኳና ከቤቱም ውስጥ ገብቶ የበሩን ቁልፍ እንደሰጠው ነው የቆጠረው:: በጭንቀት ጊዜ የሚታይ ከጭንቀት ሊያስወጣ
የሚችል መንገድ ፈተና ውስጥ ይጨምራል:: ማሪየስ በቀዳዳ ወደ ውጭ ተመለከተ፡፡ «እንሂድ» ነው ያለው በጨለማ ያናገረው ሰው:-

ልቡ በሀዘንና በጭንቀት ሲዳፈን ሕሊናው በአንድ ነገር ብቻ
ተሞልቷል፡፡ ለስቃይ እንደተፈጠረ ተገነዘበ፡፡ ለአለፉት ሁለት ወራት
ከኮዜት ጋር የፍቅርን አክርማ ሲቀጭ ነበር የሰነበተው:: አሁን ግን በድንገት ጠፋችበት፡፡ የወጣትነት ዘመን የተወሳሰበ ፍቅር ጥናትና ብርታት የደረሰበት ብቻ ያውቀዋል እንጂ በቃላት ኃይል ገልጾ በትክክል ለማስረዳት
አይቻልም:: ስለዚህ እንዲያው ዝም ነው:: ተስፋ መቁረጥ መላ አካላቱን ወረረው:: አንድ ነገር ከፊቱ ድቅን አለ፤ ከዚያ ጭንቀት፣ ከዚያ መከራ በቶሎ መገላገል፡፡

ከግቢው ወጥቶ ቶሎ ቶሎ መራመድ ጀመረ:: ዣቬር የሰጠውን ሽጉጥ በኪሱ ይዞአል፡፡ በስሙ የጠራው ሰው ከዓይኑ ተሰወረ:: በዋና ጎዳና
አድርጎ ሲጓዝ ከንጉሡ ቤተመንግሥት ደረሰ፡፡ ያንንም አልፎ ሄደ።የቤተመንግሥቱ የግቢም ሆነ የውጭ መብራቶች እንደ ወትሮው በብዛት አልበሩም:: በየመንገዱ ዳር የነበሩ ሱቆች ተዘግተዋል፡፡ ከመንገድ ዳር ቆሞ
የሚያወራ ወይም የሚጫወት ሰው የለም:: መንገድ ሁሉ ጭር ከማለቱ የተነሣ የተወረረ ከተማ መስሏል፡፡ ሆኖም የሰልፈኛ ኮቴና ጫጫታ ከሩቁ ይሰማል፡፡ ማሪየስ ተጠምዝዞ ከአንዱ ጎዳና ወደሌላው በተላለፈ ጊዜ በይበልጥ ጭር ካለ ሰፈር ደረሰ፡፡

ጉዞውን ቀጥሎ ጨለም ካለ ሥፍራ ደረሰ:: ፍርሃት ፍርሃት አለው፡፡ አንድ ሰው እየሮጠ በአጠገቡ አለፈ፡፡ «ወንድ ነዉ ወይስ ሴት?» ሲል ራሱን ጠየቀ፡፡ ለማወቅ አልቻለም:: ከገበያ ቦታ ደረሰ፡፡ የገበያውም አካባቢ
ጭር ብሉአል፡፡ የሚበራ መብራት በሩቅ ባየ ጊዜ ወደዚያ አመራ:: ቀጥሎ ከሚፈልገው ቦታ መድረሱን ተገነዘበ፡፡ ከምሽጉ ገባ፡፡ ከድንጋይ ላይ እጁን አጣምሮ ተቀመጠ፡፡ ያ እድለቢስ አባቱ ትዝ አለው:: አባቱ ኮሎኔል )
ፓንትመርሲ ጎበዝ ወታደር እንደነበር ታወሰው፡፡

እርሱም እንደ አባቱ ጉብዝናውን የሚያስመሰክርበት ጊዜ መድረሱን አወቀ፡፡ ልክ እንደ አባቱ በጥይት መካከል በመሽሎክሎክ ደፋርነቱንና ደረቱን ለጥይት ሰጥቶ ደሙን በማፍሰስ አገር ወዳድነቱን የሚያሳውቅበት ሰዓት አሁን እንደሆነ ተረዳ፡፡ ስለዚህ ጠላቱን እየተከታተለ ማጥቃት እንዳለበት
አመነ፡፡ ጦርነቱ እንዲካሄድ የታቀደው ከተማ ውስጥ ሲሆን ፍልሚያው ከሕዝብ ጠላቶች ጋር ነው፡፡ በዚህ ጦርነት ሕይወቱ እንደምታልፍ በተገነዘበ
ጊዜ መላ ሰውነቱ ተረበሸ፡፡ ሰው እንዳያየው ከጥላ ስር ተደብቆ አለቀሰ፡፡

ታሪኩ አሳዛኝ ነው:: ግን ምን ሊያደርግ ይችላል? ከኮዜት ተለይቶ ከመኖር፤ መሞት ይሻላል:: እርስዋ አገር ጥላ ስለሄደች የእርሱ በሕይወት
መኖር ትርጉም የለውም፡፡ ያን ሁሉ መንገድ ተጉዞ አሁን ካለበት ከደረሰ በኋላ ወደኋላ ማለት ትርፉ ትዝብት ነው:: በቆራጥነት መጥቶ በፍርሃት መሸሽ! ምሽጉን ፍለጋ መጥቶ ካየው በኋላ ማፈግፈግ! አይደረግም፡፡

የአሳቡ ተገዥ በመሆኑና አሁንም ልቆይ ወይስ ከዚህ ልጥፋ የሚል
ሐሳብ ስለተፈራረቀበት ወደ መሬት አቀርቅሮ ለብዙ ጊዜ ቆየ:: በድንገት ወደላይ ቀና አለ፡፡ አንድ ብሩህ የሆነ ነገር ታየው:: ከሞት አፋፍ ስንደርስ የሚታየን ዓይነት እውነታ! ልንሞት ስንል እኮ እውነት ቁልጭ ብላ ትታየናለች::

ከዚህ ፈተና ውስጥ መግባቱ እኮ የሚያስከፋ ሳይሆን የሚያስደስት
ነው:: አባቱ ለምንድነው እንደዚያ የተሰቃየው? ከባለሥልጣኖች ላይ እጅ ማንሳት እንደ ክቡር ተግባር የተቆጠረበት ጊዜ የለም እንዴ? አገሩ ከባድ ሀዘን ላይ ነው ያለችው:: ሕዝብ ደግሞ ተቃውሞውን ይደግፋል:: ፈረንሳይ
እየደማች ነው:: ነፃነት ግን ፈገግታዋን እያስታቀፈችን ነው:: የነፃነት ፈገግታ በእያንዳንዳችን ላይ ከሰፈነ ፈረንሣይ ቁስልዋን ትረሳለች::

ስፍር ቁጥር የሌለው አድልዎ፣ ግላዊ ጥቅም፣ አሉባልታ፣ ውሽት፣
መቀጫ ፣ በሥልጣን መባለግ፣ አመፅ ፣ ፍርደ ገምድልነትና የጨለማ ጉዞ ፈረንሳይ ላይ ሰፍኖአል፡፡ ይሄ ታዲያ እንዲህ የሚታለፍ ነው? ከሥረ መሠረቱ መመንገል አለበት::

ይህኛው አመለካከት ማሪየስን በደስታ ያሰከረው:: በንጉሡ ላይ እጁን እንዲያነሳ አደፋፈረው:: ምሽጉን ተዘዋውሮ ለማየት ከተቀመጠበት ብድግ
አለ:: በያለፈበት የሕዝባዊ እንቅስቃሴ አባላት ድምፃቸውን ዝቅ አድርገው ይወያያሉ::

ሰዓቱ እያለፈ ሄደ፤ አሁንም ግን ምንም ነገር የለም:: በአካባቢዎ
ከሚገኘው ቤተክርስቲያን የአራት ሰዓት ደወል ተደወለ፡፡ ኢንጆልራስና ኮምብፌሬ የካርባይን ጠብመንጃዎቻቸውን ይዘው ቁጭ አሉ፡፡ እንደተኳረፈ
ሰው አይነጋገሩም:: ምናልባት ወደ እነርሱ የሚመጣ ኃይል ካለ ጆሮአቸውን አቅንተው ለማዳመጥ ይሆናል፡፡

ጋሪ በጥድፊያ ወደ እነርሱ ሲመጣ በሩቁ ተመለከቱ፡፡ ትንሹ ልጅ
ከጋሪ ነጂው አጠገብ ተቀምጧል:: ጋሪው እየተቃረበ ሄደ:: ጋብሮች ትንፋሽ
አጥሮት ከጋሪው ላይ ዘሎ ዱብ አለ፡፡

«ጠብመንጃዬን! በጣም ተቃርበዋል» ሲል ጮኸ፡፡

ሁሉም ኮረንቲ እንደያዘው ሰው ተሸማቀቁ፡፡ ከምሽጉ የነበረ ሁሉ
ጠብመንጃውን አነሳ:: የኳኳታ ድምፅ ከያለበት ተሰማ::
«የእኔን ካርባይን ትፈልጋለህ?» ሲል ኢንጆልራስ ልጁን ጠየቀው::
«የአንተን ሳይሆን ሌላ አነስ ያለ ወብመንጃ ሰጡኝ» ሲል ጋቭሮች
መለስ፡፡

የዣቬር ጠብመንጃ ሰጡት::

ከጥቂት ጊዜ በኋላ የሰው ኮቴ ይሰማ ጀመር፡፡ ብዛት ያለው እግረኛ እንደሚመጣ በኮቴው ታወቀ:: እየተቃረቡ መጡ፡፡ በመጨረሻ ጨለማውን
ከሁለት የሚሰነጥቅ ድምፅ ተሰማ፡፡

«ማነህ?»

ወዲያው ብዛት ያለው የጠብመንጃ ቃታ ሲንቋቋ ተሰማ፡፡

«የፈረንሳይ አብዮት» ሲል ኢንጆልራስ አስተጋባ፡፡

«ተኩስ!» ተባለ፡፡
ከዚያ በኋላማ ምን ቅጡ የጥይት እሩምታ እንደ ሐምሌ ዝናብ
ወረደ፡፡ ከጣራ ለይ ተሰቅላ የነበረችው ባንዲራ ከመሬት ወደቀች፡፡

«ጓዶች» ሲል ኩርፌይራክ ጮክ ብላ ተናገረ፡፡ «ረጋ በሉ፡
ጥይታችሁን ቶሎ ቶሎ አትጨርሱ፡፡»

«ዋናው ነገር ደግሞ» አለ ኢንጆልራስ፤ «ባንዲራችንን እንደገና መስቀል
አለብን፡፡»

ከወደቀችበት አነሳው::

ማነው ጀግና ይህችን ባንዲራ ከነበረችበት መልሶ የሚተክል?»
ማንም አልመለሰለትም፡፡ ጠብመንጃ ተደቅኖበት ማነው ከምሽግ ጫፍ፡ ላይ የሚወጣ! ሪሱም ቢሆን ፈርቶአል::

«ፈቃደኛ የለም ማለት ነው!»

ምንም እንኳን መሴይ ማብዩፍ ከምሽጉ መሀል ቢሆኑም ማንም ሰው ልብ አላላቸውም:: ሆኖም ምሽጉ ሲሠራ አብረው ሠርተዋል፡፡ ሥራው ካለቀ በኋላ ከመጠጥ ቤቱ ምድር ቤት ነበር የተቀመጡት:: ቀደም ሲል
ኩርፌይራክና ሌሎችም የእርሳቸው ከዚያ መገኘት አደገኛ ሊሆን እንደሚችል ነግረዋቸው ነበር፡፡ ሆኖም እርሳቸው አልሰሙም:: የመጀመሪያው ውጊያ ሲከፈት እርሳቸው ከምድር ቤት ስላልወጡ የሆነውን አላዩም:: ሰው ሁሉ ለመዋጋት ቦታ ቦታውን ሲይዝ እርሳቸው ከነበሩበት ቀሩ። ከምድር ቤት ቀርተው የነበሩት እርሳቸው፣ ዣቬርና የዣቬር ጠባቂ ብቻ ነበሩ፡፡ እንዲያውም መሴይ ማብዩፍ ከአሳባቸው የነቁት ውጊያው ተጧጡፎ
👍11
ተኩሱ ሲጋጋል ነው:: ልክ ኢንጆልራስ «ፈቃደኛ የለም ማለት ነው!» ብሎ በመጮህ ሲናገር ድምፁን ስለሰሙ ከተቀመጡበት ብድግ አሉ። ከምድር ቤቱ ወጥተው ስው ሁሉ ከነበረበት ብቅ ሲሉ ሁሉም ዓይኑን ጣለባቸው።

«አበባ እየሸጡ የሚኖሩ ሽማግሌ አይደሉም?» ሲል ሰው ተጠያየቀ::

«እኝህማ የሕዝብ ተወካይ ናቸው» ሲል አንዱ አጉረመረመ:: እርሳቸው ግን ምናልባትም ሰው ያላቸውን አልሰሙም፡፡ በቀጥታ ወደ ኢንጆልራስ ሄዱ:: የያዘውን ባንዲራ ከእጁ ሲነጥቁ
ምሽግ ውስጥ የነበረ ሁሉ ተደናገጠ፡፡ ኢንጀልራስ ራሱ በድንጋጤ ክው አለ:: የሰማንያ ዓመት ሽማግሌ በመሆናቸው ጭንቅላታቸው ይንገዳገዳል፡፡
ሆኖም ማንም ደፍሮ ጣልቃ ሊገባ ወይም «ይተዉ» ብሎ ለመናገር
ኣልቻለም:: ከምሽጉ ጫፍ ለመውጣት በደረጃው ወደ ላይ መራመድ ጀመሩ፡፡ ከዚያ መሽጎ የተቀመጠ ሁሉ አንድ ደረጃ በተራመዱ ቁጥር በልቡ
አንድ፣ ሁለት፣ ሦስት እያለ ይቆጥር ጀመር፡፡ በጣም ያስፈራል፡፡ በድንገት
አንድ ሰው «ባርኔጣዎን ያውልቁ» ሲል ጮኸ፡፡ «ያወልቁ፣ ያውልቁ» ሲል ሁሉም ተናገረ::

ባርኔጣቸውን ሲያወልቁ ጥጥ የመሰለው ሽበታቸውና አሳዛኙ የሽማግሌ ፊታቸው በጉልህ ታየ:: ዓይናቸው ሰርጉዶአል ፧ ቆዳቸው ተጨማዷል:: ባንዲራውን ይዘው ኩራት እየተሰማቸው ከምሽጉ ጫፍ ደረሱ::

ቀና ሲሉ በሩቁ አዩ:: ምንም ዓይነት ድምፅ ግን አልተሰማቸውም:: በዚህ
ከጫፍ እንደደረሱ ከአሥራ ሁለት ሺህ በላይ የሚሆኑ ጠበመንጃዎች ፀጥታ መካከል ባንዲራውን በማውለብለብ ጮክ ብለው ተናገሩ::

«ረጅም እድሜ ለፈረንሣይ አብዮት! ረጅም እድሜ ለሪፑብሊኩ! ወንድማማችነት! እኩልነትና ሞት!»

ቀደም ሲል «ማነህ?» ሲል ጮክ ብሎ የተናገረው ድምፅ አሁንም
ጮክ ብሎ «አጥቃ» ሲል ጮኋል፡፡

የጥይት እሩመታ ተለቀቀ፡፡ መሳይ ማብዩፍ እየተንገዳገዱ ከመሬት
ተዘረሩ፡፡ በደከመ ድምፅ «እድሜ ለሪፑብሊኩ» ሲሉ ተናገሩ::
በርቀት የሚሰማው ኃይለኛ ድምፅ አሁንም «ተኩስ» ሲል አዘዘ::

የሽማግሌው ደም እንደዚያ ሲፈስ ያዩ የንቅናቄው አባሎች ፈዝዘው
ቀሩ፡፡ አንዳንድ ጊዜ እኮ በጣም ሲበዛ ራሳችንን መጠበቅ እንዳለብን ረስተን የምንፈዝበት ጊዜ አለ፡፡ የአሁኑም ከዚያ የተለየ አልነበረም:: እየተንፏቀቁ
ሄደው ሬሳውን አነሱ፡፡

«ምን ዓይነት አረመኔዎች ናቸው» ሲል ኢንጆልራስ ተናገረ፡፡

ኩርፌይራክ ወደ ኢንጆልራስ ጆሮ ጠጋ ብሎ ስለመሴይ ማብዩፍ
ማንነት ነገረው:: ከዚያም ኢንጆልራስ የሚከተለውን ተናገረ፡፡
«ወገኖቼ እኝህ ሽማግሌ በአርአያነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ እኛ አመነታን፣ እርሳቸው መጡ:: እኛ ወደኋላ ሸርተት አልን፤ እርሳቸው ወደፊት ተራመዱ:: እዩት እስቲ፤ እርጅና የሚያንቀጠቅጣቸው ሽማግሌ
በፍርሃት ለሚንቀጠቀጡ ወጣቶች ምሳሌ ሆነው ትምህርት ሲሰጡ፡፡ እኒህ ሰው እድሜ የጠገቡና የክብር ሞት የሞቱ ሰው ናቸው:: ስለዚህ የእኚህን ጀግና ሬሣ ላለማስነካት የእርሳቸውን ድፍረት ፤ የእርሳቸውን ጉብዝና ታጥቀን በቆራጥነት እንዋጋ! ይህች ምሽጋችን የማትበገርና የማትደፈር ምሽግ እናድርጋት:: »

ሁሉም በያለበት «እንዋጋለን፧ መሪያችንን አናስደፍርም» ሲል ጮኹ፡

ኢንጆልራስ ጎንበስ ብሎ የራሣውን ጭንቅላት ቀና ካደረገ በኋላ ግምባሩን ሳመው፡፡ ...

💫ይቀጥላል💫
👍13
#ገረገራ


#ክፍል_አራት


#በታደለ_አያሌው


“እንዴት ነህ ጃ?” አልሁት፣ ከተንጋለልሁበት መነሳት የእረጥብ አራስ ያህል እያቃተኝ፡፡ ያቆላመጥሁት ራሱ አልመሰለኝም ማን ብዬ ነዉ ግን የጠራሁት? እንደ እህት ጃ ነዉ ወይስ እንደ ቀበሌ ጃሪም ብዬ? እንጃልኝ
ብቻ።

“ጭራሽ አልጋዬ ላይ?”

"በይ አልጋዬን ልቀቂልኝ ያለ በሚመስል ዓይኑ ጠቅ አድርጎኝ ሲቆም፣ ብድግ ብዬ ከአልጋዉ ላይ ወርጄለት ወደ ራሴ ክፍል ሄድሁ። ምን እንዳለኝ እንኳን ልብ ያልሁት በኋላ ሻንጣዎቹን ወደ ዉጪ ማመላለስ ሲጀምር ነበር።

የእመዋ ቤት ጎስቆል ያለች ብትሆንም፣ አሠራሯ ሁልጊዜም
ያስገርመኛል። ክብ አይሏት፣ አራት ማዕዘን አይሏት፣ የግንብ አይሏት፣
የጭቃ አይሏት፣ ብቻ ግን ሁሉንም ትመስላለች። በዚያ ላይ የሞቀች
ናት፡፡ እኔም፣ ምንም እንኳን ከቤተሰባችን ጋር አባታችንን እየተከተልሁ በዞርሁበት ክፍለ ሀገር የኖርሁባቸዉ ቤቶች ሁሉ የነበረኝ ትዝታ ባይለቀኝም፣ በቅጡ ነፍስ ያወቅሁባት ቤት ናትና እንደዚችኛዋ የሚሆንልኝ ቤት ግን የለም፡፡ ጠባብ ብትመስልም ለእኛ ግን ጠብባን አታዉቅም። በዚች ቤት ሁላችንም የየራሳችን ክፍል አለን፡፡ በእርግጥ በዚች ቤት ያለንን ክፍል መጀመሪያ የያዝነዉ እንደ ዋዛ፣ በሽሚያ ነበር።
ትዝ ይለኛል፤ መጨረሻ ከነበርንበት ከተማ ቀይረን ወደ'ዚች ቤት ልንገባ ደጁን የረገጥነዉ ኅዳር 29፣ ሐሙስ ቀን ነበር።


“በሉ እንግዲህ” አለችን እመዋ፣ ልክ ወደ'ዚች ቤት በራፍ
ከመድረሳችን፣ ቤቷ ወዳሏት ክፍሎች እየለቀቀችን፡፡ “መቼም እንግዲህ አድገናል ብላችኋል። ለየብቻ ማደሩን ከሆነ የጓጓችሁለት ይኸዉ እንዳሻችሁ ሞክሩት ደግሞ። በሉ፤ ኮተቶቻችሁን በየክፍላችሁ አስገቡ”

“በየክፍላችሁ?” አልሁኝ እኔ፣ እንክት ብዬ፡ ያደግነዉ አንድ ሰፊ
ምንጣፍ መሀል ወለሉ ላይ አንጥፈን፣ ተቃቅፈን እየተኛን ነዉ። እየተኛን አልሁ እንጂ፣ የሌሊቱን እኩሌታ እንኳን የምናሳልፈዉ እንዲሁ እንዳዉካካን ነበር። ለወጉ መብራቱን እናጠፋፋና፣ ልብሳችንንም ለዋዉጠን በዚያ ሀገር በሚያህለዉ ምንጣፍ ላይ በጎን በጎናችን እንሆናለን። ከዚያ ተረቡ፣ አሽሙሩ፣ ቀልዱ፣ ተረቱ፣ እንቆቅልሹ፣ እንካ ስላንቲያዉ፣ መሳሳቁ፣ መላፋቱ ይመጣል። ያልሆነዉ ምን አለ? ዛሬ ተረኛ እኔ የሆንሁ እንደሆነ፤ አንዴ በቃል ተረብ፣ ቀጥለዉ በልፊያ፣
ቀጥለዉ ቁንጥጫ ሁሉም ይረባረቡብኛል። ታዲያ ያሉኝን ቢሉኝስ ወንድሞቼንና እህቶቼን ላኮርፋቸዉ? ኧረ በጭራሽ! እንዲያዉም አሁን አሁን ሳስበዉ፣ ተረባቸዉን እና ልፊያቸዉን ሁሉ ለመከላከል አደርገዉ
የነበረዉ መፍጨርጨር ሁሉ ሳይጠቅመኝ አልቀረም። ቢያንስ ቢያንስ ንግግሬ እና ጡንቻዬን አዳብሮልኛል። በዚያም ላይ እኮ እኔ በተራዬ የቀመስኋትን ሁሉ፣ እነሱም በየተራቸዉ ይቀምሷታል።

“በየክፍላችሁ? አረ ምን ዓይነት፣ የማን ሐሳብ ነዉ ግን ይኼ?” አልኋት እመዋን፣ ሆዴን ባር ባር እያለዉ።

“ቀርፋፎ! ይልቅ ተመርጦ ሳያልቅብሽ ክፍልሽን አትመርጪም?” አለችኝ
ኣንደኛዋ እህቴ፣ የራሷን ክፍል መርጣ ማንም እንዳይነካባት ቆልፋዉ ወደኔ እየተመለሰች።
ብቻዬን እንደ ቀረሁ አስተዋልሁ። ሁሉም ይሻለኛል የሚለዉን ክፍል
ተሻምቷል። እኔ እዚህ በትዝታ ወዲያ ወዲህ ስል፣ እንደ ዱሯችን
እንድንተኛ እንድመካከራቸዉ እንኳን የሚሆን አፍታ ሳይታገሱኝ መስኮት ያላቸዉን እና በመስኮት በኩል አሻግሮ ለማየት የሚያመቹትን ክፍሎች ሁሉ ተሽቀዳድመዉባቸዋል፡፡ በተለይ የጃሪም ደግሞ ልዩ ነዉ፡፡ ከመስኮት በተጨማሪ፣ በዚህ በኩል ወደ ዋናዉ ሳሎን የሚያስገባ እና በዚያ በኩል
ደግሞ ወደ ዉጪ የሚያስወጣ በር ያለዉን፣ ሰፊዉን ክፍል ነዉ ተሻምቶ የያዘዉ።

ምንም አማራጭ ስላጣሁ እነሱ ያያዟቸዉን ክፍሎች እየተዟዟርሁ
ስመለከት ቆይቼ፣ ያሉኝን ኮተቶች ሁሉ እየጎተትሁ ወደ ተተወችልኝ
ምራጫ ክፍል አስገባሁባት። ያም ሆኖ ግን እምብዛም አልከፋኝም ነበር። ምክንያቱም፣ ዞሮ ዞሮ ወንድሞቼ እና እህቶቼ ናቸዉ። ለስሙ ክፍሉ የየራሳቸዉ ቢባልም፣ መቼም በፈለግሁት ክፍል እንዳላድር የሚከለክለኝ
አይኖርም፡፡ እነሱም ለጊዜዉ መስሏቸዉ ነዉ እንጂ፣ በዚህ ምርጫቸዉ እንደሚጸጸቱ ገምቻለሁ። ለአንድ ወይም ላኹለት አዳር ለየብቻ ከሞከሩት
በኋላ ወደ መሀል ወለል መጥተዉ እንደ ዱሯችን አብረን እንተኛ
ማለታቸዉ አይቀርም፡፡ ይኼን ይኼን ሳስብ ትንሽ ቀለል ብሎኝ የነበረ ቢሆንም፣ ዉሎ አድሮ የሆነዉ ግን እንደ ጠበቅሁት አይደለም።

ይኼዉ በእንደዚያ ያለ ሁኔታ የያዝነዉ ክፍል አሁንም ድረስ ድርሻችን እንደሆነ አለ። የኋላ በኋላም ቢሆን፣ ጨክነን የየራሳችንን ቤት ስላልሠራን፣ በዚሁ ቤት ያለዉ ክፍላችን እንደ ተጠበቀ አለ። በርግጥ ገሚሶቹ ወንድሞቼ ወጣ ገባ እያሉ የኪራይ ቤት ኑሮ የሞካከሩ አሉ።
የሆነዉ ሆኖ፣ አሁን የየራሳችንን ሥራ ከያዝን እና የየራሳችን ኃላፊዎች ሆነናል ካልን በኋላም የምንኖረዉ እዚሁ ግቢ ነዉ። ቀን የየራሳችንን ሥራ ስንከዉን ዉለን አዳራችንም በየራሳችን ክፍል፣ በየራሳችን አልጋ ሆኗል። በእርግጥ እኔ ከሌሎቹ በተለየ መልኩ፣ ክፍት ባገኘሁት አልጋ
ሁሉ ነዉ የምተኛዉ። እንዲያዉም ብዙ ጊዜ ክፍት ሳይሆንም ጭምር፣ ጠጋ በሉልኝ ብዬ አብሬ የምተኛበት ጊዜ አለኝ። እያየኋቸዉም እንኳን
ደርሰዉ ንፍቅ በሚሉኝ ሰዓት ስስቴን የማስታግሰዉ፣ እነሱን እቅፍ አድርጌ ትንፋሻቸዉን ስምግ ያደርሁ እንደሆነ ብቻ ነዉ። እንደ ነፍሴ በምሳሳላቸዉ እህቶቼ እና ወንድሞቼ አልጋ ላይ ብተኛ፣ ነዉሩ ምን ላይ እንደሆነ አሁንም አይገባኝም፡፡ በእርግጥ ማንም ከልክሎኝ አያዉቅም ነበር። እኔ እንዲያዉም ደስ የሚላቸዉ ነበር የሚመስለኝ።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ማጉረምረም አመጡ፡፡ አንዳንዶች እንደ ጨዋታ እያስመስሉ፣ አንዳንዶች ደግሞ የሆነች የጀመሯት ነገር አልሳካ ያለቻቸዉ
እንደሆነ፣ ቀድመዉ የሚያላክኩት ወደኔ ሆኗል። የእነሱ ማለት የእኔም ነዉ እያልሁ ባደረስኝ ክፍል ሁሉ ስንት እና ስንት ልብስ እና ጌጣጌጥ ያኖርሁ ቢሆንም፣ አሁን ግን እሱን ጭምር ብላሽ አስቀርተዉብኛል።

“ምነዉ ሻንጣህን ሸካከፍህ፣ ንብረት እያሸሽህ ነዉ'ንዴ ወንድሜ?” አልሁት፣ በእኔ ቤት ቀልጄ ሞቼ ልቤ ዉልቅ እያለ፡፡ ይኼም አልበቃ ብሎኝ እኮ ጥርሴን ለፈገግታ አግጥጨዋለሁ ሳላስበዉ ነፍሰ ጡር እንደሆንሁ፣ ሕይወቴ ምስቅልቅሉ እንደወጣ፣ የእሱ የወንድምነት ምክር
እንደሚያስፈልገኝ ልነግረዉ በልቤ ወስኛለሁ። በመሆኑም የመጨረሻ
ሻንጣዉን አንጠልጥሎ ወደ በሩ ሲጣደፍ ተከተልሁት። ለካንስ ሌላ
ደልዳላ ሰዉ ደግሞ ከበሩ በእዳሪ ሆኖ እየተቀበለ ወደ መኪናዉ
እያጓጓዘለት ኖሯል። ልብ ባልለዉ እንጂ፣ ከልብሶቹ ሌላም የእኔ ናቸዉ የሚላቸዉን እቃዎች ከሳሎን ሳይቀር ለቃቅሞ በመኪናዉ ቀርቅቦ አስጭኖ ጨርሷል። አልጋዉን ራሱ ከምን ጊዜዉ እንዳወጣዉ አላየሁትም።

“ምን እያደረግህ ነዉ አንተ?” አልሁት፣ ልሳቅ አልሳቅ በሚል ቃና።

“ቻዉ!” አለኝ፣ ጥያቄዬን እንዳልሰማ ሁሉ የመኪናዉን የጋቢና በር ከፍቶ እየገባ፡፡

“አንተ ጃሪም! ቆይ እንጂ ወዴት ... ምን እየሆንህ ነዉ?” አልሁት፣
ተንደርደሬ ከፊት ለፊቱ መንገዱን ዘግቼ እየቆምሁበት።

“አይበቃንም ብለሽ ነዉ?”

“ምኑ ነዉ የሚበቃን?”

“ዉሽቱ ሁላ! ለጥቅማችሁ ስትሉ ጠብ እርግፍ አላችሁ እንጂ፣ እኔ እኮ ከዚህ ቤተሰብ አይደለሁም። እናትሽም እናቴ፣ አንቺም እህቴ፣
ዘመዶችሽም ምኔም አይደላችሁም በቃ”

“ምንድነዉ የምታወራዉ?”
👍342
“አሁንማ አንቺ እና እናትሽ እንዲህ ዓለማችሁን የምትቀጩበት ቤት
የአባቴ ቤት መሆኑን አዉቂያለሁ። ለጊዜዉ ትቼላችሁ ወጥቻለሁ። መቼ ተመልሼ እንደምመጣ አልነግራችሁም። ብቻ ያኔ እዚህ ካገኘኋችሁ ነዉ ጉዱ”

ቀልድ ነዉ ቢለኝና ሰማዩን በሳምሁት፤ እሱም ባልበቃኝ፡፡ ነገር ግን ዓይኑ ላይ ጥላቻዉን አኑሮ ያንቺ እህትነት በቅቶኛል አለኝ በምሬት:: ወንድምነት ደግሞ ያበቃል እንዴ? ልክ በስምምነት እንዳገኘነዉ ተራ ነገር፣ እህትነትም በቃኝ ሊሉት ይቻላል ለካ? ያዉም ከአንድ አብራክ የተካፈለኝ የእናቴ ልጅ?

እዉነትም ፈተናዉን ሲያመጣዉ አያድርስ! አሁን እኔ በየትኛዉ
ምክንያት ነዉ ማበድ ያለብኝ? መቼም ማበዴ ላይቀር ነዉ እንግዲህ፡፡የሕይወቴ ዓይነተኛ ምሰሶዎች ሁሉ፣ ዓይኔ እያየ ተሰባብረዉብኛል።

«ምንድነዉ እናንተ?” አለችን እመዋ፣ የግቢዉን በር ከርፈድ አድርጋ ስትገባ ከጃሪም ጋር እንደ ተዋጊ ፍየሎች ተፋጠጥን ብትደርስብን። አንደኛዋ እህታችን እና ሌላኛዉ ወንድማችንም ተከትለዋት ገቡ። እሷ ከቤተ ክርስቲያን፣ እነሱ ደግሞ ከጋራ ሱቃቸዉ ሲመለሱ በአጋጣሚ
መንገድ ላይ ተገናኝተዉ እንደሚሆን እገምታለሁ።

“አትናገሩም ወይ?” አለች እመዋ፣
እየተራመደች።

“ልጅሽን አንድ በዪልኝ!” አልን እኩል፣ እኔም ጃሪምም።

“ሆሆሽ” ብላ እርጅና ወስዶባት በተረፉላት ጥርሶቿ ሳቀችብን።
“ሁልጊዜ ልጅነት አለንዴ እናንተ? በሉ ይልቅ እንዲያ እንዲያ በሉና
ምሳ ነገር አቀራርቡ። አንዳችሁ ደግሞ ጀበና ጣዱ እስኪ። በሉ
አልኋችሁ እኮ!” አለችንና ባሞጨሞጩ ዓይኖቿ ጨርቁሳን አለፈች።

በዚህ ዕድሜያችን እቃ እቃ እየተጫወትን መስሏታል እመ። እንደ እዉነቱማ ቢሆን፣ ከዚህ በላይ ቀልድ እኮ በየትም አይገኝም። ኧረ ወንድምና እህት ነን ኧረ አይደለንም ብሎ መለማመንን የመሰለ ጨዋታ ምናለ? አብረዋት የገቡት እህት እና ወንድማችን፣ ግብግቡ
ሲጀመር ሰልፋቸዉን ከማናችን ጋር እንደሚያደርጉ እያሰቡበት ነዉ
የሚመስሉት። አንድ ጊዜ እኔ ላይ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ ጃሪም ላይ አፍጥጠዉ ይጠባበቃሉ።

“ጉዳችሁን ሰማችሁ?” አልኋቸዉ፣ የእመዋን ወደ ቤት መግባት
ጠብቄ፡፡ “ወንድማችሁ አይደለሁም ብሏችኋል እንግዲህ”

“እ?” አሉ ኹለቱም፣ ፍርጥም ብለዉ፡፡

“ደም እና ነፍስ እንጂ፣ ወሬኛ ይመስል ወንድም እና እህት ያደረገን፣
‹ሰዉም ቢሆን ከመሬት ተነስቶ አያወራም፤ እዉነትም እመ እናቴ
አትመስለኝም ነዉ የሚለዉ እንግዲህ”

“ምን ምን ምን?” አለ ከእመዋ ጋር የገባዉ ወንድሜ፣ ሳቁ አጓጉል
ጥርሶቹ ላይ ከስሎበት።

“እርማችሁን አዉጡ ...”

“እስኪ አንቺ ዝም በይ!” ብላ እህቴ አፌን አስያዘችኝ፡፡ መቼም ሐሜቱን ቀድማም ሳትሰማዉ የቀረች አትመስለኝም። እሱ ብቻ ሳይሆን እሷ ራሷም
የቤተሰቡ አካል እንዳልሆነች ሲወራባት ነዉ የባጀችዉ። እንዲያዉም አልፎ አልፎማ፣ ካህኑ አባታችን በቁመተ ሥጋዉ እያለ በየክፍለ ሀገሩ ተዘዋዉሮ የማገልገሉን ነገር እየጠቀሱ፣ ከየቦታዉ ልክ እንደ ርካሽ ሸቀጥ
እንደ ለቃቀመን ሁሉ ይወራል። ጭራሽ እመዋም አባታችንም መካኖች እንደሆኑ፣ እህ ብለዉ የወለዱት ልጅ እንደ ሌላቸዉ የሚቀባጥሩም አሉ። ለእኔ ለራሴ ሳይቀር እህቶቼ የምርም እህቶቼ እንዳይደሉ ሊያሳምኑኝ የደፈሩ አሉ። በእናቴ ሆድ ሳላ ጀምሮ የማዉቀዉን፣ እሹሩሩ ብዬ
ያሳደግሁትን የታናሼን ታናሽ ሳይቀር ወንድሜ እንዳይደለ
ተወራርደዉብናል፡፡

“ገና ለገና ሰዉ አወራ ተብሎ...” ስል፣

“ዉብርስት!” ብላ ጮኸችብኝ። እንደገና ጸጥ አሰኘችኝ፡፡ ትንፋሼን ሳይቀር ነዉ የዋጥሁት፡፡ የምወዳትን ያህል እንደ ታላቅነቷ ደግሞ እሰማታለሁ፡፡እታዘዛታለሁ። አሁንም ወደ ቤት እንድገባ በዓይኗ ስትገፈትረኝ፣ ያለ ምንም ወለም ዘለም ነዉ ሹክክ ብዬ የገባሁት። በበኩሌ ጃሪም ዓይን ዓይኔን እያየ በዚህ በዚህ ምክንያት ነዉ የተጠራጠርሁት ቢለኝማ፣
አስተካክየለት የልቡን ባደርስለት ደስታዉንም አልችለዉ። እንግዲህ ምን ማድረግ እችላለሁ? እሱን ራሷ እህታችን እንደ ፍጥርጥሯ ታድርገዉ! ከፈለገች አባብላ፣ ካልሆነ አስፈራርታ፣ ያም ቢቀር ተደራድራ ወደ ቤት ትመልሰዉ ይሆናል። ወዲያዉም እኮ እኔ ራሴ የራሴ ራስ ምታት ያለብኝ
ሰዉ ሆኛለሁ።

በራሴ ቡዳ የተሰለቀጥሁ ብኩን ሴት አይደለሁ? የራሴዉ ጣጣ ይበቃኛል፡፡

ልክ ስገባ የእጅ ስልኬ እሪ ብሎ እየጠራኝ ደረስሁበት፡፡ ዓይኔን ወርወር አድርጌ ስመለከተዉ፣ አሁንም ለስንተኛ ጊዜዉ እንደሆነ እንጃለት ባልቻ እየደወለ መሆኑን አየሁ። አላደርገዉም እንጂ ባነሳዉ ግን ምን ሊለኝ
ኖሯል? መቼም እንደ ንጹሕ ሰዉ እንዲያ በሩ የመብረቅ ድምፅ
እስከሚወጣዉ ድረስ ከደፉ ጋር አላትሜባቸዉ ከመጣሁ በኋላ፣ ከሊቀ መንበሩ ጋር ሳይቦጭቁኝ የቀሩ አይመስለኝም። ምን ብለዉኝ ይሆን በማርያም? በተለይ ባልቻ እንዴት ይሳቀቅብኝ ይሆን? ስለተጫወትሁበት
ሕይወቴ በሰማ ጊዜ ሰማይ ምድሩ አይዞርበት ይሆን? አንገቱን ነዉ ያስደፋሁት። «በሰዉ መመካት አይገባም፣ ከተመካሁ ግን ማን እንደ ዉብርስት ብሎ አፉን ሞልቶ በኩራት እንዳላወራልኝ ሁሉ፣ ይኼን
ጉዴን ባወቀ ጊዜስ መሸሽጊያ አያጣብኝ ይሆን? እንኳንስ ለእሱ ቀርቶ በሩቁ ለሚያዉቀኝ ሁሉ ማፈሪያ ሆኛለሁ በቃ።

ከዚህ በኋላ ያየኝ ሁሉ ቤተ ክርስቲያን ግቢ እንደ ገባች ዉሻ ቢያሯሩጠኝ፣ የማልፈርድበት መሆኔን እያሰብሁ ሳለ ኩልል የሚል እንባዬን ለማበስ
አንድ መዳፍ ጉንጬ ላይ አረፈብኝ። ማን አጠገቤ እንዳለ ለማወቅ ግን ዓይኔን መግለጥ አይጠበቅብኝም፡፡ እመዋ ናት። ልጇ በተክሊል ከብሬ
የምታይበት ቀን አልደርስልሽ ብሏት ስትጓጓ፣ ተበላሽቼ ያሳቀቅኋት እናቴ ናት በርኅራኄ አጠገቤ የቆመችልኝ፡፡

እመዋ”

“ንገሪኝ ም'ሆነሻል?”

“አዋረድሁሽ አይደል?” አልኋት፣ እግሯ ሥር እየወደቅሁ።
አላቃናችኝም፡፡ ይልቁንም በትክክሌ በዘፈቀደ ተቀምጣ፣ አንገቷ ሥር ሸሸገችኝ፡፡

“አንቺ እኔን? ምናርገሽ?”

“አፈርሁኝ። አሳፈርሁሽ። ሐፍረቴን ደግሞ አወቀሽብኛል፣ አርግዣለሁ። ማሪኝ እመ”

“ቆይ እስኪ...”

“ከዚህ በላይ ምን ልበድልሽ እችላለሁ? ባስቀመጥሽኝ ቦታ አልተገኘሁም እኮ። እንዳሳደግሽኝ፣ እንደ ጠበቅሽኝ መቼ ተገኘሁ? ምንኩስናም
ተክሊሉም ቢቀር፣ እንደ ባህሉ እንደ ወጉ እንኳን እልል ያላስባልሁበት፤ የትዳር አጋሬ ይኼ ነዉ ብዬ ካላስተዋወቅሁሽ፣ ‹የልጄ አባት ይኼ ነዉ ብዬ ከማልናገርለት ሰዉ ነዉ እኮ ያረገዝሁት”

“ከእሸቴ ማለትም አይደል?”

“እ?”

እሸቴ ነዉ ያለችዉ? ቆይ እሷ የማታዉቀዉ፣ እኔ ምን እነግራታለሁ ከዚህ ሌላ? ድርቅ አድርጋ ነዉ ያስቀረችኝ፡፡ ደግሞ ስሙን በመስማቴ እንደገና ሽቅብ ሽቅብ አለኝ፡፡ አቅለሸለሸኝ፡፡ ቅርንት፣ ክርፍት አለኝ፡፡

“እሽቴን ደግሞ የት አወቅሽዉ?” አልኋት፣ እንደ ምንም ትንፋሽ ወስጄ።

“ተጣልተሽዋል ለካ?”

“ማን? ነገረሽ?”

“እሸቴ። በእርግጥ ስለጠባችሁ እንኳን ምንም ያለኝ የለም። የራሴዉ ግምት ነዉ። ብቻ ይኼዉ ኹለት ሦስት ወር ያልፈዋል፤ ተመላልሶ እኔን ያልጠየቀበት ዕለት አልነበረም። ግሩም ልጅ ገጥሞሻል። ቡሩክ ልጅ!”

“አይ ቡሩክ ልጅ'ቴ! ወይ አለማወቅሽ!” አልኋት፣ በማሽሟጠጥ።የሴተኛ አዳሪ ጭን ሱሰኛ መሆኑን ብነግራት ቅስሟ እንዳይሰበር ፈራሁላት። እንዳልተወዉ ደግሞ ለእሱ ያላት ግምት አናደደኝ፡፡ ስለዚህ
ካልሁት አይቀር፣ ገመናዉን አፍረጥርጬ ልናገርለት ይገባል።

“ለመሆኑ ምን አጣላችሁ?”

“እንደምትገምቺዉ አይደለም ልጁ። እንዲሁ በቆዳዉ ስታይዉ ቡሩክ መስሎሽ ይሆናል እንጂ ራሱ ተልከስክሶ እኔንም ጽሞና አልባ ያደረገኝ እሱ ነዉ”

«ማን? እሽቴ?”

“እመዋ አፈር ስሆንልሽ”
👍23😁2🥰1
እ?”

"ስሞትልሽ ስሙን አትጥሪብኝ!”

“እንደዚያ ያለ ልጅ እንኳን አይመስልም። ይሁንና አሁን ግን የት ነዉ ያለዉ? ብቅ ካለ እኮ ዉሎ አደረ”

“የት አዉቄለት”

“ምንድነዉ የት አዉቄለት ብሎ ነገር? ይሁንና የቅድሟን ነገር የት
አደረግሻት? እስኪ አምጫት”

“የቷን ነገር?”

“እህእ? ቅድም እዚያ ከበዓታ ስንለያይ እቤት አኑሪልኝ ብዬም
አልሰጠሁሽ?”

“እ...” ብዬ ጎስጉሼ አኑሬበት ከነበረዉ የራሷ አልጋ ትራስጌ ሥር
አዉጥቼ ሰነዘርኩላት፡፡ አልተቀበለችኝም፡፡

“ያንቺ ነዉ” አለችኝ፣ እኛ እያለን ራሷ ወደ ጀመረችዉ የምሳ ጉድ ጉዷ እየተመለሰች፡፡ “ታዲያ አደራሽን ምንድነዉ ቅብጥርሴ እንዳትጠኝ። እኔ ምኑንም አላዉቅልሽም። ስጭ ነበር የተባልሁት፣ ይኼዉ ሰጥቼሻለሁ።
አበቃሁ” በእራፊ ጨርቅ የተጠቀለለች ትንሽ ነገር መሆኗን ቀድሞዉንም ስትሰጠኝ
ኣስተዉያለሁ፡፡ ምን እንደሆነች ለማየት ገለጥ ባደርጋትም፣ ጥቅልሉ ስለበዛ ፍሬ እቃዋን ቶሎ ልደርስበት አልቻልሁም፡፡ ስቀበላት እምነት መስላኝ ነበር። አይደለችም ማለት ነዉ? በዚያ ላይ ስንት ዙር እንደ
ተጠቀለለች! ተርትሬ ተርትሬ ስጨርስ ያገኘሁት ግን ጥፍር እንኳን የማታህል ሚሞሪ ካርድ ብቻ ነበረች፡፡ መጠቅለያ ጨርቁን ባራግፈዉም፣ ከእሷ ሌላ ምንም የለም። እመዋ ደግሞ እንዳልጠይቃት ቀድማ መንገዱን
ሁሉ ዘጋግታብኛለች፡፡ ምን ቸገረኝ ብዬ ወደ ሞባይሌ ቀፎ ከተትኋት።

ይቀጥላል
👍24
#ምንዱባን


#ክፍል_አርባ_ስድስት


#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ

....ኢንጆልራስ ጎንበስ ብሎ የራሣውን ጭንቅላት ቀና ካደረገ በኋላ ግምባሩን ሳመው፡፡
መሞቱን በመርሳት በጥንቃቄ ያልያዘው እንደሆነ የሚያምመው ይመስል ቀስ ብሎ በክርኑ ደግፎ ቀና አደረገው፡፡ የሟቹን
ኮት ካወለቀ በኋላ የሚደሙትን ቀዳዳዎች ለተመልካች አሳየ።

«ይሄ ነው ባንዲራችን!»

ነጭ አንሶላ አምጥተው የመሴይ ማብዩፍን አስከሬን ሸፈኑት:: ስድስት ሰዎች ጠብመንጃዎቻቸውን ከስር አጋድመው ሬሣውን ከዚያ ላይ ካሳረፉ በኋላ ወደ ምድር ቤት በዝግታ ወስደው ከትልቅ ጠረጴዛ ላይ አጋደሙት፡፡ ሰዎቹ በሚፈጽሙት ተግባር ቅዱስነት በመዋጥ አደገኛ ሁናቴ ውስጥ
መሆናቸውን ጨርሰው ረሱ::

አስከሬኑ ከዣቬር ከታሰረበት ግንድ አጠገብ ሲያልፍ ኢንጆልራስ
ሰላዩን አናገረው::

«የምትቀጥለው አንተ ነህ::»

በዚህ ጊዜ ብቻውን የጥበቃውን ተግባር ያከናውን የነበረው ጋብሮች ሰዎች ከምሽጉ ውስጥ ሲገቡ ውልብ አለው:: በድንገት ጩኸት ተሰማ::

‹‹ተጠንቀቁ!»

የአድማው መሪዎች በሙሉ ዘልለው ወደ ውጭ ወጡ:: የሚያባክኑት ጊዜ አልነበራቸውም:: ወታደሮች ሳንጃቸውን ወድረው ከምሽጉ ሲገቡ ተመለከቱ፡፡

ያቺ ሰዓት ወሳኝ ነበረች:: ምሽጉ በንጉሡ ወታደሮች ተወረረ::
በመጀመሪያ ዘልሎ የገባው ወታደር ከውስጥ የነበረ አንድ ሰው ግምባሩን ብሎ ጣለው:: ገዳዩ ወዲያው በጠላት ወገን ወታደር ተገደለ:: አሁንም ሌላ
ወታደር ከርፌይራክን ከመሬት ስለዘረረው እንደወደቀ «እርዱኝ» እያለ ጮኸ፡፡ በዚያው ወቅት እጅግ በጣም ግዙፍ የሆነ ወታደር ጋቭሮች ከነበረበት ክፍል ገባ፡፡ ጋቭሮች ጠብመንጃዋን ከዣቬር ወደ ወታደሩ አዙራ ለመተኮስ
ቶሎ ብላ ቃታውን ሳብ አደረገች:: ግን ምን ይሆናል ዣቬር ጠብመንጃውን ሲሰጥ ለካስ ጥይት አላጎረሰው ኖር ፀጥ አለ፡፡ ወታደሩ ከት ብሎ ሳቀ፡፡
ሳንጃውን ወድሮ ወደ ልጁ ሄደ::

ወታደሩ ልጁ ዘንድ ከመድረሱ በፊት ከኋላው ስለተመታ በአፍጢሙ ተደፋ:: ወዲያው ከርፌይራክን የመታው ወታደር ሲወድቅ ታየ፡፡ ሁለቱን
ሰዎች የገደላቸወ ማሪየስ ነበር፡፡
ማሪየስ የመጀመሪያውን ውጊያ በሩቁ ሆኖ ሰውነቱ እየተንቀጠቀጠ
ነበር ያየው:: በሁለተኛው ግን የጋብሮችን ሕይወት በመጀመሪያ ሲያድን ጓደኛውን ቀጥሎ ነው ነፃ ያወጣው፡፡ ኩርፌይራክ ከመሬት ወደቀ እንጂ አልተመታም ነበር፡፡

ወታደሮቹ ከምሽጉ ሁለት ሦስተኛ የሚሆነውን ክፍል ከቁጥጥራቸው
ሥር አውለዋል፡፡ በጣም ወደ ውስጥ ዘልቀው ለመግባት ግን አልደፈሩም:: ምናልባት አንድ ዓይነት ወጥመድ ቢኖር ብለው ተጠራጥረዋል። በዚያ !
አካባቢ ይበራ የነበረው መብራት እስከ ውስጥ ዘልቆ አያሳይም::

አንድ ወታደር ማሪየስን ለመጣል ሲያነጣጥር ድንገት ከመሀል አንድ ሰው በመግባቱ የእርሱን እጣ ሰውዬው ወሰደ:: ወዲያው በድንገት አንድ በጣም የሚጮህ ድምፅ ተሰማ::

«እጃችሁን ስጡ ፤ አለበለዚያ ምሽጉን እንዳለ እናቃጥለዋለን፡፡»

አድምኞቹ ሁሉ ድምፁ ወደ ተሰማበት አቅጣጫ ፊታቸውን አዞሩ፡፡ ማሪየስ ከየት መጣ ሳይባል ይህን ያለውን የሃምሣ አለቃ ስለጣለው ምሽጉ ከመጥፋት ዳነ፡፡

አድመኞቹ በሙሉ ማሪየስን ከበቡት:: ኩርፌይራክ ከወደቀበት ተነስቶ ከአንገቱ ላይ ተጠመጠመ
«እንዴት ያለ አጋጣሚ ነው» አለ ኮምብፌሬ::

«ጥሩ ጊዜ ደረስክ» አለ ቦስዩ ቀጠለና::

«አንተ ባትደርስ ይህን ጊዜ በሕይወት የለሁም» አለ ከርፌይራክ።

«እኔ ደግሞ ይህን ጊዜ በአፍጢሜ ተደፍቼ ነበር» አለ ጋቭሮች ቀጥሎ፡፡

ወዲያው አንድ ድርጊት በመፈጸሙ ደስታቸው በሀዘን ተለወጠ። ከመካከላቸው በጣም የሚወዱትና የሚያደንቁት አንዱ ጓደኛቸው ተሰወረ። ከቁስለኛ መካከል ፈለጉት:: ከዚያ አልነበረም:: ከሞቱት መካከል አዩት ከዚያም አልነበረም፡፡ ተማርኳል ማለት ነበር፡፡

«ወንድማችንን ወሰዱት፤ እኛ የእነርሱን መኮንን እንደያዝን ሁሉ
እነርሱም ጓደኛችንን ያዙት ማለት ነው:: በሰላዩ ላይ ስለምንወስደው
እርምጃ ወስነናል?» ሲል ኮምብፌሬ ኢንጆልራስን ጠየቀው፡፡

«አዎን» አለ ኢንጆልራስ የኮምብፌሬን ትከሻ እየነካካ፡፡ «ሆኖም የሰላዩ ደም የጓደኛችንን የዣን ጥሩቬርንን ደም አያህልም፡፡»

«እንግዲያውማ» አለ ኮምብፌራ «መሐረቤን ከጠመንጃዬ ጫፍ
አስሬ ልውጣና ሰላዩን በጓደኛችን እንዲለወጡን ልጠይቅ::»

«ስማ» ብሎ ኢንጆልራስ ሲናገር ከውጭ አንድ ድምፅ ተሰማ፡፡
የወንድ ድምፅ ነበር::

«ፈረንሣይ ለዘላለም ትኑር!»

የጓደኛቸው ድምዕ እንደሆነ አወቀ፡፡ ጥይት ተተኩሰ፡፡ ከዚያም ሁሉም ነገር እርጭ አለ::

«ጓደኛችንን ገደሉት!» አለ ኮምብፌሬ:: ኢንጆልራስ ወደ ዣቬር ዞር ብሎ «ጓደኞችህ አሁን አንተን ነው የገደሉት» አለው::

አድመኞቹ ሁሉ አሁን ከቤት ወስጥ ገብቷል:: ማሪየስም
ተከትሉኣቸው ሊገባ ሲል «መሴይ ማሪየስ» ተብሎ ስሙ ሲጠራ ሰምቶ በመደንገጥ ዞር አለ፡፡ ከሁለት ሰዓት በፊት ኮዜትን እየጠበቀ ሳለ ከአጥር ውጭ ሆኖ የጠራው ድምፅ እንደሆነ አውቋል፡፡ ማን እንደሆነ ለማወቅ
ፊቱን ቢያዞርም መለየት አልቻለም:: «እዚህ ነኝ» አለ ያው ድምፅ በጣም የደከመ በመምሰል፡፡

መሬት ለመሬት እየተንፏቀቀ የሚመጣ ሰው በሩቁ ተመለከተ፡፡
መብራት ካለበት ሲደርስ የሴት ሸሚዝ የለበሰ ሰው መሆኑን አየ:: ከስር የተቀዳደደ ሱሪ ታጥቋል፡፡ ጫማ አላጠለቀም፡፡ ይህ ፍጡር ማሪየስ ከነበረበት ሲደርስ የገረጣ ፊቱን ቀና አደረገ፡፡

«አታውቀኝም?»
«የለም»
«ኢፓኒን፡፡»
ማሪየስ ቶሎ ብሎ ወደ መሬት አጎነበሰ፡፡ እውነትም ያቺ እድለቢስ
ኢፖኒን ነበረች፡፡ እንደ ወንድ ነው የለበሰችው::
«እንዴት መጣሽ?» ከዚህ ደግሞ ምን ትሠሪያለሽ?
‹‹መሞቴ ነው» ስትል መለሰችለት::
ማሪየስ ደንግጦ «ተመትተሻል እንዴ?» ሲል ጠየቃት::
ከመሬት ብድግ ሊያደርጋት ቀኝ እጁን ከወገብዋ ስር አስገባ፡፡ ብድግ ሲያደርጋት እጅዋ ተዝለፈለፈ:: የማቃሰት ድምፅ አሰማች፡፡
«አሳመምኩሽ?»
«ትንሽ»
«ምነው እጅሽ ዛለ?» ብሎ" ሲያየው በጥይት ተመትቷል፡፡
«ቆስሎአል፧ አይደለም?»
«አዎን፡፡»
«ማን መታሽ?»
«ከጥቂት ጊዜ በፊት ጠብመንጃ ተደቅኖብህ ልትመታ ስትል አንድ
ሰው ከመሀል መግባቱ ትዝ ይልሃል?»
«አዎን፣ አስታውሳለሁ::»
የእኔ እጅ ነው ጣልቃ የገባው::
የማሪየስ ልብ ከሁለት የተሰነጠቀ መሰለው:: ነገሩ አልገባውም::
ምነው እንደዚያ አደረግሽ! ምስኪን! ብቻ ቁስሉ ለክፉ አይሰጥሽም።
ለማንኛውም ከውስጥ አስገብቼ ላስተኛሽ፡፡»
እጄ ብቻ እኮ አይደለም የተመታው:: ጥይቱ በእጄ አልፎ ከብብቴ ጥቂት ዝቅ ብሉ ወደ ወገቤ በመግባቱ ቀስፎ ይዞኛል» አለች በኃይል ለመተንፈስ እየታገለች::

«ስለዚህ ወደ ውስጥ መግባቱ ዋጋ የለውም:: አሁን ብቻ ከአጠገቤ ቁጭ ብለህ አጫውተኝ፡፡ ጨዋታህ ከሐኪም እርዳታ ይበልጥብኛል፡፡»

ትእዛዝዋን ተቀብሎ እግሩን በመዘርጋት ከአጠገብዋ ቁጭ አለ።

ጭንቅላትዋን ከጉልበቱ ላይ አሳረፈች:: ቀና ብላ ሳታየው «እፎይ ተመስገን እንዴት ይመቻል? ምን ዓይነት ደግ ሰው ነህ! በቃ! ሕመሙ ተቀነሰልኝ
ስትል ቀባጠረች፣::

ከዚያም ለጥቂት ጊዜ ፀጥ አለች:: ቀስ ብላ ፊትዋን ወደ ማሪየስ
አዙራ ቀና ብላ አየችው::

«አስቀያሚ ናት ነው ያልከው፤ አይደል? » ንግግርዋን በማቆም ጥቂት ዝም ካለች በኋላ እንደገና ቀጠለች::
👍19
«መቼስ አሁን አልቆልሃል:: ከዚህች ምሽግ ማንም በሕይወት
አይወጣም:: እኔ ነኝ፧ ከዚህ እሳት ውስጥ የጨመርኩህ:: እርግጠኛ
ነኝ አንተም ትመታለህ:: ሆኖም ሰውዬው ጠብመንጃውን እነጣጠር ሊገድልህ ሲል እጄን አፈሙዙ ላይ በማድረግ አዳንሁህ:: ይህንንም ያደረግሁት
ከአንተ በፊት ለመሞት ፈልጌ ነው፡፡ ከተመታሁ በኋላ በደረቴ እየተንፏቀቅሁ ከዚህ ስመጣ ማንም አላየኝም፡፡ ማንም ደግሞ ከወደቅሁበት አላነሳኝም::
አንተን ነበር የምጠብቀው:: ነገር ግን ከወደቅሁበት እንደማትመጣ አወቅሁ፡፡በመካከሉ እኔ በጣም ተሰቃየሁ፡፡ አሁን ግን ተሽሎኛል:: ከቤትህ መጥቼ ሰውነቴን አንተ ቤት ባለው መስታወት ያየሁበት ቀን ትዝ ይልሃል? ደግሞስ መንገድ መገናኘታችን ትዝ ይልሃል? አንተ እንኳን አንድ መቶ ሱስ
ስትሰጠኝ «ገንዘብህን አልፈልግም ብዬ እንኳን መለስኩልህ! ለመሆኑ ገንዘቡን
መሬት ስጥለው መልሰህ አነሳኸው? ሀብታም ስላልነበርክ መቼስ አትተወውም፡፡ ታዲያ መሴይ ማሪየስ ፤ ሁሉንም አስታወስክ? አቦ እንዴት
ደስ አለኝ! ሁላችንም ልንሞት ነው::
ዓይንዋ ተቅበዘበዘ፡፡ አሳብዋ ተንቀዋለለ:: እጅዋን ሊጠቀልልበት ከደረትዋ አካባቢ ሸሚዝዋን ቀደደ:: ደረትዋን ሲገልጥ ጥይት የገባበት ቦታ
በግልጽ ታየ:: ደም ይወጣው ነበር፡፡ ማሪየስ ያቺን እድለቢስ ልጅ ዝም ብሎ አፍጥጦ አያት::

«ወይኔ» ስትል በድንገት ጮኸች፡፡ «ሕመሙ እንደገና መጣ፡፡ ምነው
አፈነኝሳ!» ከለበሰችው ልብስ አንዱን ክፍል አፍዋ ውስጥ በመጉሰር ንክስ አደረገችው:: እግሮችዋ ተንቀጠቀ፡፡

«እባክህን አትሂድ» አለችው:: «አሁንማ ረጅም ጊዜ አይሆንም:: :

ብድግ ብላ ቁጭ አለች:: ድምፅዋ ግን እየሰለለ ሄዶ ውጪ ነፍስ ግቢ
ነፍስ ሆነ:: እንግዳ በሆነ ድምፅ በማቃሰት ትናገር ጀመር፡፡

«ስማ፤ ለአሞኝህ አልፈልግም:: ኪሴ ውስጥ የአንተ ደብዳቤ አለ::
ትናንትና እንድሰጥህ ተሰጥቶኝ ነበር፡፡ ግን እኔ ዘንድ አቆየሁት:: ላገኝህ አልፈልግሁም ነበር:: ምናልባት ቶሉ ቶሎ ስንገናኝ ደስ አይልህ እንደሆነ ብዬ ነው:: ሆኖም ተገናኘን አይደል? ደብዳቤህን ውሰድ::»

በሚደማው እጅዋ ማሪየስን እጅ አፈፍ አደረገችው፡ የቁስሉ ሕመም
አልተሰማትም:: እጁን ይዛ ከኪስዋ ውስጥ ጨመረችው:: ኪስዋ ውስጥ የነበረውን ወረቀት በመንካቱ፡ ደብዳቤ እንዳለ ማሪየስ አመነ::

«ውሰደው » አለችው::

ማሪየስ ደብዳቤሁን አወጣ:: የደስታ ምልክት የፊትዋ አሳየችው::

«ለስቃዩ ስትል አሁን ቃል ግባልኝ::»

«ምን ብዬ?»ሲል ማሪየስ ጠየቃት::

«ቃል ግባልኝ፡፡»

«ቃሌን ሰጥቻለሁ፡፡››

«ከሞትኩ በኋላ ግምባሬን እንድትስምልኝ ቃል ግባልኝ፣ ስትስመኝ ደግሞ ይሰማኛል፡፡»

ማሪየስ ጉልበት ላይ ተደፋች፡፡ ዓይንዋን ጨፈነች፡፡ ያቺ ምስኪን
የሞተች መሰለው፡፡ ኢፓኒን ሳትነቃነቅ ዝም ብላ ቆየች፡፡ ማሪየስ «አሁንስ የዘላለም እንቅልፍ ወስዷታል ብሎ ሲያስብ ነቅነቅ አለች፡፡ ዓይንዋን ለመግለጥ ሞከረች፡ የሞት ጥላ አጥልሎባታል፡፡ ከዚያ በዝግታ ከወትሮው በተለየ ድምፅ አናገረችው፡፡»

«ማሪየስ ከአንተ ፍቅር እንደያዘኝ አምናለሁ፤ አንተ ግን ይህን ታውቅ
ኖሮአል?»

ፈገግታ ለማሳየት ሞከረች፤ ግን አልቻለችም፣ ነጐደች፤ ለዘላለም
ሄደች፡፡

ማሪየስ ቃሉን አከበረ፡፡

የቀዘቀዘውን ግምባርዋን ምጥጥ አድርጎ ሳመው፡፡ ነገር ግን ኮዜትን መክዳቱ አልነበረም፡፡ ያንን የተከፋ ነፍስ ለመሰናበት የፈጸመው ተግባር ነበር፡፡

ደብዳቤው ትዝ አለው:: ለማንበብ ቸኮለ፡፡ ወዲያው ልጅትዋ እንደ
ሞተች ደብዳቤውን ገልጦ ለማየት ጓጓ:: ይኸው ነው የሰው ልጅ ጠባይ።ለእርሱ የሚሆን ምን ነገር እንዳለ ለማወቅ ይቸኩላል፡፡ ከመሬት ላይ በዝግታ አስተኝቶኣት ከዚያ ተነስቶ ሄደ::

የሻማ መብራት ወደ ነበረበት ምድር ቤት ወረደ:: በሚገባ የታሸገ አነስተኛ ደብዳቤ ሲሆን እሽጉ የሴቶች ጥንቃቄ የታከለበት ይመስላል።

በፖስታው ላይ የተጻፈው አድራሻ የራሱና የጓደኛው የከርፌይራክ ነበር። ቶሎ ብሎ ፖስታውን ቀድዶ ማንበብ ጀመረ::

«የእኔ ፍቅር፣ የሚገርምህ ነው፤ አባዬ አሁኑኑ እንድንሄድ ይፈልጋል። ዛሬ ማታ ሆም አርሜ ከተባለ ሥፍራ እንሄዳለን:: በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ከእንግሊዝ አገር እንገባለን፡፡ ኮዜት፣ ሰኔ 4፡፡»

ደብዳቤውን ከሳመው በኋላ አጣጥፎ ፖስታው ውስጥ ጨመረው። የፍቅርዋን ጽናት በማረጋገጡ ደስ አለው:: ሁልጊዜም ቢሆን የሌላው ወገን
ፍቅር ብርታትና ጽናት ማወቅ ያስደስተናል፤ ለመወደዳችን ማረጋገጫ ነውና::

«መሄድዋ ነው ፤ አባትዋ ይዟት ሊሄድ ነው:: አያቴ ደግሞ እንድንጋባ አልፈቀዱም፡፡ ምንም የተለወጠ ነገር የለም» ሲል እርስ በራሱ ተነጋገረ፡፡ እንደ ማሪየስ ያለና በቅዠት ዓለም ውስጥ የሚኖሩ ሁሉ የዚህ ዓይነት
ሁናቴ ሲገጥማቸው በሀዘን ተጨማልቀውና ተስፋ ቆርጠው የማይሆን መንገድ በመምረጥ ከማይሆን መደምደሚያ ላይ ይደርሳሉ፡፡ ሕይወት መሯአቸው በቶሎ መሞትን ይመርጣሉ፡፡ ይህም በመሆኑ ማሪየስ ሁለት
ነገሮችን ብቻ መፈጸም እንዳለበት ይወስናል፡፡ ይኸውም ስለመሞቱ ለኮዜት መግለጽና የመጨረሻውን የስንበት ቃል በመልእክተኛ መላክና የዚያችን የምስኪን የኢፓኒን ወንድም ማለት የሚስተር ቴናድዩ ወንድ ልጅ ከዚያ
አስከፊ አደጋ ማውጣት ነበር፡፡
የማስታወሻ ደብተሩን ከኪሱ አወጣ፡፡ አንድዋን ቅጠል ቀድዶ
የሚከተለውን ጻፈ::

«ጋብቻችን አልሆነም:: አያቴን ስጠይቃቸው እንድንጋባ አልፈቀዱም:: እኔ እንደሆነ ምንም ዓይነት ሀብት የለኝም:: አንቺም ብትሆኚ ከእኔ አትሻይም::
ወደ ቤት መጥቼ ነበር፧፧ ግን አላገኘሁሽም:: ምን ብዬ ቃል እንደገባሁልሽ
የምታውቂው ነው:: ቃሌን አከብራለሁ፤ እሞታለሁ፣ እወድሻለሁ፡፡ ይህን
ደብዳቤ ስታነቢ ነፍሴ ከአጠገብሽ ትሆናለች፤ እናም በፈገግታ ታይሻለች፡፡»
ደብዳቤውን የሚያሽግበት ፖስታ አልነበረውም፡፡ ስለዚህ ወረቀቱን
አጣጥፎ አድራሻዋን ጻፈበት:: ማስታወሻ ደብተሩን ወደ ኪሱ መለሰ፡፡ ከዚያም ጋብሮችን ጠራው:: ልጁ እየሮጠ ወደ ማሪየስ ሄደ:: «ውለታ
እንድትውልልኝ ብጠይቅህ እሺ ትለኛለህ?» ሲል ማሪየስ ልጁን ጠየቀው::
«እንዴታ» ሲል ልጁ በፈገግታ መለሰለት፡፡ «እግዚኣብሔር
በሚያውቀው ኣንተ ባትደርስልኝ ኖሮ አሁን እኮ የሞትኩ ሰው ነበርኩ፡፡»
«ይህን ደብዳቤ ታየዋለህ?»
«አዎን፡፡»
«እንካ ያዘው:: በቶሎ ከዚህ ምሽግ ውጣና ሂድ::» ጋቭሮች በመገረምና
በመረበሽ ፀጉሩን አከከ፡፡
«ነገ ጠዋት ደብዳቤውን በአድራሻው ለኮዜት ስጥልኝ::»
እስከ ነገ ምሽጋችንን ይይዙታል፡፡ ታዲያ ሲይዙት እኔ ከዚሁ ለመሆን
እፈልጋለሁ አለ ልጁ በኩራት መንፈስ፡፡
«እስኪነጋ ድረስ ሁለተኛ ምሽጋችንን አያጠቁም:: ስለዚህ ምናልባትም እስከ ነገ እኩለ ቀን ድረስ ምሽጋችን ከእጃችን አትወጣም::»

«እሺ እንግዲያውስ» ሲል ልጁ መለሰ፡፡

ልጁ በሩጫ ከዚያ ወጥቶ ሄደ:: ከዚያ ሲሄድ አንድ አሳብ ነበረው::
ግን ለማሪየስ የነገረው እንደሆነ የሚቃወመው ስለመሰለው አሳበን ሳይገልጽ ነው የሄደው:: አሳቡም ይህ ነበር፡፡

«እኩለ ሌሊት እንኳን አልሆነም:: ኮዜት ያለችበት ሰፈር ደግሞ
እስከዚህም ሩቅ አይደለም:: ደብዳቤውን አሁኑኑ እወስድላታለሁ፡፡ ከዚያም
በቶሉ እመለሳለሁ::......

💫ይቀጥላል💫
👍212
Forwarded from Eyos bot
💎 የናንተን ቴሌግራም profile 👤 ማን በብዛት እንዳየው ማወቅ ይፈልጋሉ!
profile ፎቶአቹን የሚያየውን ሰው ስም ዝርዝር ለማግኘት እነዲሁም ስንት ጊዜ እንዳየውና የቱን "save" እንዳረገው ለማወቅ ከፈለጉ 👇"START"የሚለውን ይንኩት!
👍4👎2🤔1
Forwarded from 🌹 ፍቅሬን-በ-ግጥም 🌹
🔞. መርየም ብለው ይጠሩኛል...

ወጣት እና መልከ መልካም ልጅ ነበርኩ። በዩኒቨርሲቲ ትምህርት ላይ ሳለሁ ከአንድ የሌላ አገር ወጣት ጋር ተዋወቅኩኝ። እሱም የአገሬ ልጅ ካለመሆኑም ባሻገር በሁኔታዎችም አሰገዳጅነት በብዛት እየተገናኘን አንድ ላይ በመሆን አብረን እናሳልፍ ነበር ።

ከመጀመሪያ የግንኙነት ጊዜያችን ጀምሮ በሃሳብ ደረጃ በደንብ ተግባባን ቀናቶች እያለፉ በመጡ ቁጥር ግንኙነታችን ይበልጥ እየተጠናከረ መጥቶ መለያየት ከባድ ሆነብን። ይህንን የሰሙ የሀገሬ ልጆች በኔ ላይ ሴራን ይሸርቡ ጀመር። አንድ ቀን ከዶርም በመውጣት ላይ ሳለሁ በጣም የሚዘገንን ነገር ሰሩብኝ። ያን እለት የሆንኩት አስታውሼ መናገር ይከብደኛል። እጅግ ሚሰቀጥጥ ድርጊት ነበር። ከዶርም ስወጣ …see more read
👍7👏2😁21
#ገረገራ


#ክፍል_አምስት


#በታደለ_አያሌው

.....“ያንቺ ነዉ” አለችኝ፣ እኛ እያለን ራሷ ወደ ጀመረችዉ የምሳ ጉድ ጉዷ እየተመለሰች፡፡ “ታዲያ አደራሽን ምንድነዉ ቅብጥርሴ እንዳትጠኝ። እኔ ምኑንም አላዉቅልሽም። ስጭ ነበር የተባልሁት፣ ይኼዉ ሰጥቼሻለሁ።
አበቃሁ” በእራፊ ጨርቅ የተጠቀለለች ትንሽ ነገር መሆኗን ቀድሞዉንም ስትሰጠኝ
ኣስተዉያለሁ፡፡ ምን እንደሆነች ለማየት ገለጥ ባደርጋትም፣ ጥቅልሉ ስለበዛ ፍሬ እቃዋን ቶሎ ልደርስበት አልቻልሁም፡፡ ስቀበላት እምነት መስላኝ ነበር። አይደለችም ማለት ነዉ? በዚያ ላይ ስንት ዙር እንደ
ተጠቀለለች! ተርትሬ ተርትሬ ስጨርስ ያገኘሁት ግን ጥፍር እንኳን የማታህል ሚሞሪ ካርድ ብቻ ነበረች፡፡ መጠቅለያ ጨርቁን ባራግፈዉም፣ ከእሷ ሌላ ምንም የለም። እመዋ ደግሞ እንዳልጠይቃት ቀድማ መንገዱን
ሁሉ ዘጋግታብኛለች፡፡ ምን ቸገረኝ ብዬ ወደ ሞባይሌ ቀፎ ከተትኋት።
ከዚያም በድምፅ ማጫወቻዉ ከፈትሁት፡፡ ከትንሽ የነፋስ እና የወፎች ጺዉጺዉታ በኋላ፤ ማሲንቆ የሚያስንቅ አንቺሆዬ ዓይነት ፉጨት መጣ፡፡

የት ነበር የማዉቀዉ ይኼን ድንቅ ትንፋሽ?

መቼ አጣኋቸዉ! ወይዘሮ ብርሃኔ ናቸዉ፡፡ እሳቸዉ ናቸዉ ትንፋሻቸዉን እንደ ፈለጉ የሚያሽሞነሙኑት። እንኳን በሴት በወንድ እንኳን የማላዉቀዉን፣ ማንኛዉንም ዜማ በፉጨታቸዉ ብቻ ሲያወጡት አያድርስ ነዉ። በዘለሰኛ ጨዋታቸዉ የሁሉን ነፍስ የሚገዙት፣ በሸክላ ሥራ ጥበባቸዉ ሁሉን የሚያስደንቁት፣ ፉጨት እና ሽለላዉን
የሚያዉቁበት፣ ወይዘሮ ብርሃኔ ናቸዉ። አትጠገቤዋ፣ ደርባባዋ ሰዉ! በእርግጥ መጀመሪያ ያወቅኋቸዉ በእሸቴ በኩል ነበር። የእሱ እናት ናቸዉ፡፡ እንደ ጣና ሐይቅ የተረጋጉት፣ እንደ ዥማ ወንዝ የልብ የሚያደርሱት ሴት ናቸዉ በፉጨት የመጡብኝ። ጥሎብኝ አንጎራጓሪ ሰዉ
አይሆንልኝም፡፡ እጅግ አድርጌ እወዳለሁ። በተለይ ዘለሰኛ! ዘለሰኛ ለመስማት ስል ምንም ነገር ቢሆን እተዋለሁ። አሁን አሁን እንዲህ እሸቴ የሚባል ስም በአፍንጫዬ ይውጣ ልል፣ ያኔ ልቤን ወለል አድርጌ
እንድከፍትለት ካደረገበት ብዙ ምክንያቶቹ አንዷ እናቱ ነበሩ።

ልዩ ናቸዋ!

ፉጨቱን ተከትሎ በድምፃቸዉ ደግሞ መጡብኝ። ያ ከእሕልም
ከመጠጥም የሚጣፍጠዉ ዘለሰኛቸዉ!

ኧኧኧኧኧኧ...
ሸክላ ሠሪ አርገህ ሾመኸኛል
የሸክላ ጥበብ ይገባኛል፡፡
ኧኸ

ሸክላ ማለት የእጄ ሥራ
እኔ ደግሞ የእጅህ ሥራ፤
የእጄ ተሰብሮ ብመኝም ሞት
የእጅህን ማትረፍ ግን አወቅህበት!

ኧ ኸ ኧ ኸ ኧ.....

ምንም እንኳን ቀረጻዉ ጥራት ያልሞላለት ሆኖ ሞገዱ እንደሚዋዥቅበት ሬዲዮ ወስድ መለስ ሲያደርገዉም፣ እየደጋገምሁ አጣጣምሁት። ከምኔዉ እንደሆነ እንጃልኝ ብቻ አሁን መረጋጋት ይታይብኛል። አሁን ከፋኝ ብዬ ስነፈርቅ አልነበር እንዴ? ፊቴን ዳበስሁት፤ እንባ የሚባል ጠብታዉ ሳይቀር የለም። ወደ መስታዎት ሮጬ ዓይኔን አየሁት። እንኳንስ ደም
ሊመስል! ልክ ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉ ወደ ነባሩ ቀልቤ ተመልሻለሁ። ያውም ወደ ደስተኛዋ ዉብርስት። ጃሪም የለ፣ እሸቴ የለ፣ እርግዝና የለ
ሁሉም ደህና። ፍጹም ሰላም፡፡

“እመዋ?” አልኋት፣ እንጀራ ይዛ ወደ ሳሎን ብቅ ከማለቷ፡፡

ለወጉ ያህል ብቻ ቀና ብላልኝ፣ ወደ ማዕድ ቤት አልፋኝ ሄደች። ምን ላርግሽ፣ ይልቅ ማቀራረቡን አትረጅኝም? ማለቷ መሰለኝ። ከምኔዉ እንዲህ እንደ ተረጋጋሁ እሷንም ሳይደንቃት አልቀረም።

“ማነዉ የሰጠሽ ግን?” አልኋት፣

እግር በእግር እየተከታተልኳት።
“ማን ይመስልሻል?” አለችኝ፣ ፍርጥም ብላ።

“ብቻ እሽቴ ነዉ እንዳትዪኝ በማርያም”

“እሸቴ የሆነ እንደሆንስ? ስጦታ ሁሉ ያዉ ስጦታ አይደለም ወይ?”
“እህእ?”
ስጦታ ሁሉማ ያዉ አይደለም፡፡ ከእሸቴ ነዉ ማለት ነዉ? እንደ ፈራሁት መልሶ ከፋኝ፡፡ እንደገና ስምጥ ወደ ሆነዉ ድባቴ ዉስጥ ተወርዉሬ ወደቅሁ። መቼም ከእሱ ሌላ የእናቱን ድምፅ ቀርጾ በእናቴ በኩል የሚልክልኝ አይኖርም፡፡ ለዚያዉም ድምፁ ሌሊት ወፍ ጭጭ ሲል በድብቅ የተቀረጸ ነዉ የሚመስለዉ። ስለዚህ አብሮ የሚያድር ሰዉ ነዉ ማለት ነዉ የቀረጻቸዉ፡፡ ያም ሰዉ ከእሸቴ ሌላ ሊሆን አይችልም፡፡ እሱ
ነዉ የላከልኝ። እጅ መንሻ መሆኑ ነዉ? የተጣላነዉ በእናቱ ይመስል፣ በዚህ ሊያባብለኝ መሞከሩ የበለጠ እልህ ዉስጥ ጨመረኝ፡፡

እናቱ ሌላ፣ እሱ ሌላ።

ራሴን ግን ታዘብሁት፡፡ ቶሎ የሚከፋኝ፣ ቶሎ የምደሰት ግልብ ሆኜ አርፌዋለሁ ማለት ነዉ በቃ? አሁን ለቅሶ፣ አሁን ሳቅ፣ እንደገና ለቅሶ?
ሰአሊ ለነ ቅድስት!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሐዘንም ሐፍረትም ቀላቅሎ ከመታኝ ይኸዉ ቀናት አለፉ፡፡ ያዉም እንደ ሙጀሌያም እየተሙጀለጀሉብኝ። በእነዚህ ቀናት ሁሉ በእመዋ ቤት ተደብቼ ራሴን አዳመጥሁት። እንደ ወትሮዬ ወደ አደባባይ ሳልወጣ፣
እንደ ድሮዉ በወዳጅ ሳልከበብ፣ እንደ ሁልጊዜዉ ወደ ሲራክ-፯ ማዕከል ሳልመላለስ ዐሥራ አንድ ረዣዥም ቀናት እያለፉኝ ሄደዋል። እንዲሁ አልፎ አልፎ ብቻ ሲልብኝ፣ ክራሬን አንስቼ ለብቻዬ እያንጎራጎርሁ በእናቴ ቤት ሰነበትሁ፡፡

በዚህ ምክንያት እመዋም ሁኔታዬን እያየች ስትብሰለሰል፣ እያሳዘነችኝ መጣች፡፡ ምናልባት ዘወር ብልላት ይቀላት እንደሆነ ብዬ፣ ሲራክ-፯ ለአንዳንድ ተልእኮዎች በማሰብ በምስጢር ቀድሞም ወደ ተከራየልኝ
ምስጢራዊዋ ቤት ደግሞ ሄድሁ። ይቺ ቤት፣ በተልእኮዬ ሂደት መሀል
እንድቀራረባቸዉ የሚያስገድዱ ሰዎች ቢኖሩ ቤቴ ብዬ የማሳያቸዉ ቤት ናት። እንደ ሁኔታዉ፣ እነዚህ ዒላማ የተደረጉ ሰዎች ረዥም ጊዜ እና የተለየ መቀራረብ የግድ የሚፈልጉ ስለሚሆን፣ የቤት ቡና የምጋብዛቸዉ በእመዋ ቤት ባለኝ ክፍል ሳይሆን፣ በዚሁ ምስጢራዊ የኪራይ ቤት ነዉ።

ወደ'ዚህ ቤት እንደመጣሁ፣ እመዋ አዘዉትራ እሸቴ ምን በደለሽ?»
ስትለኝ የሰነበተችዉ ጥያቂ ድንገት ሽዉ አለችብኝ፡፡ ገና ዛሬ፣ አሁን ገና። እንደገና አስብሁበት:: እዉነትስ ግን እሱ ምን በድሎኛል? ምንም። ምንም ወንጀል አጣሁበት። ቆይ እኔ ራሴ አይደለሁ እንዴ፣ ዓለም በቃኝ ብሎ
ከመነነበት የእናቱ ከተማ ሄጄ የተዋወቅሁት? እኔ ባልሄድበት እንኳንስ መበደል፣ ጭራሽ የት ያዉቀኝ ኖሯል? ደረስሁበት እንጂ አልደረሰብኝም እኮ፡፡ ይልቅስ ራሴ ነኝ በገዛ ሕይወቴ የተጫወትሁት። እኔን ማንም አልበደለኝም። ከተበደልሁም የተበደልሁት በራሴ ነዉ። እኔዉ ነኝ ራሴንም እግዚአብሔርንም የበደልሁት። ስለዚህ ራሴን ለካህን ማሳየት
አለብኝ።

ንስሐ ያስፈልገኛል።

ወዲያዉኑ ተስፈንጥሬ ተነሳሁና፣ ነጠላዬን እንደ ነገሩ አንገቴ ላይ ጥዬ ወደ መኪናዬ ሮጥሁ። ምስጢራዊዋ ቤቴ በአዲስ አበባ ልዩ ሰፈሩ ልደታ በሚባለዉ የምትገኝ ኮንዶሚኒየም ስለሆነች፣ ተዘግቶ እስከሚከፈት
የሚያጉላላኝ የአጥር በር የለብኝም፡፡ ይቺን መከራ ቻይ መኪናዬን ዛሬም ያለቅጥ ረግጬ አበረርኋት። የትራፊክ መብራት የሚባል ለቅጽበት አላስቆመኝም። ንስሐ አባቴ የሚያገለግሉት እዚሁ ልደታ ጎን ባለዉ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ቢሆንም፣ በዚህ አመሻሽ ግን እሳቸዉ የት
እንዳሉ አላዉቅም። በቤታቸዉ ሊሆኑ እንደሚችሉ በመገመት ነበር ቀጥታ ወደ መኖሪያ ቤታቸዉ የሄድሁ። እዚያ ስደርስ ግን አጣኋቸዉ።

አቤት ጥድፊያ! ስልክ ቁጥራቸዉ አለኝ አይደል እንዴ?
ደወልሁላቸዉ።
“እዚያዉ ልደታ እኮ ጉባዔ ላይ ነበርሁ። ምናለ ከመድከምሽ ፊት ደዉለሽ ብትጠይቂኝ ኖሮ ልጄ?” አሉኝ፣ በሐዘኔታ፡፡

“ግድየለም፡፡ እዚያዉ ልምጣ ታዲያ?”

“ምን ገዶኝ? ነይ በይ እዚሁ”
👍352
ከምኔዉ እንደ ደረስሁ። ከቅጽሩ ገብቼ፣ ለአርምሞ ወደሚያዘወትሩበት
ሥፍራቸዉ ስሄድ፣ የግላቸዉን የሠርክ ጸሎት ጀምረዉ አገኘኋቸዉ።ፈንጠር ብሎ በሚገኝ ለስላሳ ድንጋይ ላይ ተቀምጩ ጠበቅኋቸዉ።

“መጥተሽ ነወይ ፍቅርተማርያም? እንደምን አምሽተሻል?” አሉኝ፣
ከረዥሙ ጸሎታቸዉ መልስ።

ተመስገን!

ምኑንም ሳላስቀር ዝክዝክ አድርጌ ተናዘዝሁላቸዉ። መቼም ንስሐ ከገባሁ በኋላ እንደማገኘዉ ያለ ዕረፍት በሌላ በምንም አላገኝም፡፡ አረፍሁ። በዚያዉም ላይ፣ በክርስትና እምነት አንዴ ተጸጽቶ ንስሐ የተቀበሉበትን ኃጢአት እያወሱ ማዘን፣ ክህደት እንደሆነ አባቴ ራሳቸዉ ደጋግመዉ
ነግረዉኛል። መሐሪ ነዋ አምላካችን! የሆነዉ ሁሉ ሆኖ አልፏል በቃ። አለቀ፡፡ የተቀበልሁትን ቀኖና መፈጸም እና ስለ ይቅር ባይነቱ ማመስገን
እንጂ፣ ከእንግዲህ ማለቃቀስ አይገባኝም፡፡ አጠፋሁ ይቅርታ ለመንሁ
ይቅርታ አገኘሁ። አበቃ::

ቅልል ብሎኛል።

“ምስጢር ልንገርሽ?” አሉኝ፣ መስቀል ተሳልሜ የንስሐ አባቴን
ይፍቱኝ ብዬ ልሰናበታቸዉ ወደ ጉልበታቸዉ አፌን ሳሞጠሙጥ። ቆም ብዬ ጠበቅኋቸዉ። አፍ አፋቸዉን እያየሁ ለመስማት ብጠባበቅም፣ እሳቸዉ ግን ለማጓጓት ይመስላል፤ ምስጢር ያሉትን ለመናገር ሆነ ብለዉ
አዘገዩብኝ፡፡ እዉነትም ጓጓሁላቸዉ። ለነገሩ ምስጢር መስማት የማያጓጓዉ ማን አለ? ሰዉ በምንም ዓይነት ስሜት ዉስጥ ቢሆን እንኳን፣ ምስጢር
ከተባለ ጆሮዉ መቆሙ የማይቀር ነዉ። ያዉም ከካህን ልብ አምልጦ
የሚገኝ ምስጢር! በጣም ጓጓሁ።

“ቀድሞሻል”

“ማን?”

እሸቴ”

ኧረ በስመ አብ! የዚህን ልጅ ስም የማልሰማበት ቦታ የለም በቃ? በእርግጥ እሳቸዉን እንኳን እሸቴን እንዴት አወቁት ማለት አልችልም። እኔ ራሴ ነኝ የንስሐ አባት ይኑርህ ብዬ እሳቸዉ ዘንድ አምጥቼ እሸቴን ያስተዋወቅኋቸዉ፡፡ እኔ ለስንትና ስንት ቀናት እንደዚያ ቀኑ
ሲጨልምብኝ፣ አጅሬ እሽቴ ቀድሞኝ ንስሐ በመግባቱ አደነቅሁት። የትና የት ጥሎኝ ሄዷል፡፡ በልጦኛል፡፡ የንስሐ አባቴ ግን ጉዴን ያዉቁ ኖሯል ማለት ነዉ? ታዲያ ምነዋ ቀድመዉ ቢነግሩኝ? ቢያንስ ደዉለዉ ልጄ
ጠፋሽብኝ ሊሉኝ አይገባም ነበር? አይዞሽ ብለዉ ማጽናናት
አልነበረባቸዉም?
“አታኩርፊ” አሉኝ፣ የዉስጤን ሁሉ እንደሚያዉቁበት አዉቀዉብኝ::
“ራስሽ እንደምትመጪ ስለማምን ነበር እንዲህ ነዉ እንዲህ ነዉ ሳልል የጠበቅሁሽ። ጸጸት ከዉስጥ ሲሆን አይዶል ዋጋ የሚኖረዉ?”

አሳመኑኝ፡፡ እንኳንስ እንደኔ ላለ ትዕቢተኛ ይቅርና ማንም ቢሆን ጥፋቱን ማመን ያለበት ራሱ ጥፋተኛዉ ነዉ። ጥፋት የሆነዉንና ያልሆነዉን ለይቶ የማስተማር የካህኑ ድርሻ ሲሆን፣ ይኼን ይኼን በድያለሁ፣ ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቁኝ ብሎ ካህን ፊት መዉደቅ ግን የኔ ፋንታ ነዉ። ያለበለዚያማ ምኑን ኑዛዜ ሆነዉ? መቼስ እንደ መርማሪ ፖሊስ
አይመረምሩኝ።

እሳቸዉ ልክ ነበሩ። አበጁ!
ክብረ ንጽሕናዬን እንደ ዘበት ማጣቴን ካወቅሁባት ዕለት ጀምሮ እሽቴ በደረሰበት ላለመድረስ ያልሞከርሁት መሸሸጊያ ጭንብል የለም፡፡ እሱም እኔ ያለሁበት ቦታ እንዳይደርስ ያልሠራሁበት ተንኮል የለም። በተለይም ዕለት በዕለት ሊያገናኘን ይችል ከነበረዉ የሲራክ-፯ ማዕከል ያስወጣሁበት
ሴራ ትዝ ብሎኝ ፈገግ አልሁ።
በደንቡ እንደሚታወቀዉ፣ አንድ ሰዉ የማኅበሩ አባል ለመሆን ኹለት መሠረታዊ ቅድመ ግዴታዎች ተቀምጠዉለታል። በቅድሚያ ከጀርባዉ ምንም የቅሰጣ እከክ የሌለበት ክርስቲያን መሆን፣ ሲቀጥል ደግሞ
የማኅበሩን መተዳደሪያ ደንብ ተገንዝቦ መቀበል ይጠበቅበታል። ከዚያ በኋላ በሕዝብ ዘንድ በግላጭ ከሚታወቁት እና እጅግ ከበሬታ ካላቸዉ የማኅበሩ የአገልግሎት ማዕከላት በአንደኛዉ ገብቶ ማገልገል ይጀምራል።
ይኼ ለማኅበራችን ማኅበርተኞች ሁሉ የሚሠራ ሲሆን፣ ደንቡም
የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቀጥተኛ ይሁንታ አለዉ። ሕዝብም ሆነ
መንግስት ይኼንን ጠንቅቀዉ ያውቁለታል። ከማኅበሩ ማዕከላት አንዱ፣ የመረጃና ደኅንነት ጉዳይ የሚመለከተዉ ሲራክ፯ ግን እንኳንስ በሰፊዉ ሕዝብ ይቅርና በራሱ በማኅበሩ ማኅበርተኞችም አይታወቅም። በጣም ከጥቂቶች በቀር፣ ሲራክ ፯ን የሚያዉቀዉ ራሱ እግዚአብሔር ብቻ ነዉ።
ስለሆነም የሲራክ ፯ አባል ለመሆን እንደ ሌሎቹ ማዕከላት በምርጫ የሚገኝ አይደለም። ይልቁንም ራሱ ማዕከሉ ነዉ አባሎቹን በሥዉር ከማኅበሩ አባላት መካከል መርጦ የሚመመለምለዉ። ምልመላዉም እጅግ ዘለግ ያለ ሂደት አለዉ። አንድ ዕጩ አባል ወደ ማዕከሉ መመልመል ሲጀመር፣ ቅድሚያ ከአፍ መፍቻ ቋንቋዉ ተጨማሪ፣ ቢያንስ ኹለት የሀገር ዉስጥ ቋንቋዎች እንዲማር ይደረጋል። በኹለተኛነት ደግሞ መደበኛ ሙያዉ ምንም ሆነ ምን ለስድስት ወራት ያህል ወደሚመደበበት
ገጠር ሄዶ በሙያዉ እንዲያገለግል ግዳጅ አለበት። በዚያም ለኗሪዎቹ የሚያበረክተዉ በጎ ሥራ ታይቶ፣ ነጥብ ይሰጠዋል። ያመጣዉ ነጥብ
ከተወደደለት ብቻ ወደ ከተማ ተመልሶ ተጨማሪ የመስክ ልምምድ ይጀምራል፡፡ በእርግጥ የተመለመለዉ ለመረጃ ሰብሳቢነት ሊሆንም ላይሆንም ይችላል። ቢሆንም ባይሆንም ግን ቀጥታ ወደ ታጨበት ንኡስ
ክፍል ዘሎ መግባት የለም።

በሁሉም ምዕራፎች ደግሞ የጎንዮሽ ሥልጠናዎች እና ግዴታዎች አሉ።

ሂደቱ እንደዚህ ቢሆንም፣ እሸቴ የተመለመለዉ ግን በመደበኛዉ የሲራክ ፯ የምልመላ መንገድ አልነበረም። እሱ እንዲያዉም ከነጭራሹም የማኅበሩ አባል አልነበረም:: አባል አለመሆን ብቻም ሳይሆን፣ ማኅበሩን
ከነስሙ ይጠላዉ ነበር። ማንም ያልታደለዉን ዕዉቀቱን ለመጠቀም ሲባል ብቻ፣ በቀጥታ ነዉ የሲራክ ፯ አባል እንዲሆን የተደረገዉ፡፡ እኔም እሱን የመረጃ ማዕከሉ አባል በማድረግ ሂደቱ ላይ እንዲያ ከፍ ዝቅ እንዳላልሁ
ሁሉ፣ ማየት ባስጠላኝ ጊዜ ደግሞ ከሲራክ ፯ ላማስባረር ያልፈነቀልሁት ድንጋይ አልነበረም። በመጨረሻም ተሳካልኝ፡፡ ባልቻ የሲራክ ፯ ዋና ኃላፊ ሆኖ የተሾመ ዕለት በቡና ሰዓት ስንጨዋወት፣ የምመኘዉን ዜና አበሠረኝ፡፡

(እሸቴ ወደ ባንቱ ሊሄድ መሆኑን አዉቀሻል ወይ? አለኝ፡፡
‹ እረ በጭራሽ! የት ነዉ ደግሞ ባንቱ?)


(አሃ. ለእሱ እኮ ተነግሮታል። እንዴት አልነገረሽም?)

(የት አባቱ!) አልሁኝ በለሆሳስ፣ ዞር ብዬ ለልቤ ደስታ እያጠጣሁት።
ለይስሙላ እንደማያዉቅ ሆንሁበት እንጂ፣ ለምን ጉዳይ እና ለምን ያህል ጊዜ ባንቱ እንደሚሄድ ሳይቀር ጠንቅቄ አዉቃለሁ፡፡ እንደገና እንደ ዕጩ
አባል ተቆጥሮ የስድስት ወሩን የገጠር የግዳጅ አገልግሎት ለመወጣት፣ በደቡብ ምዕራብ በኩል በምትገኘዉ ባንቱ መመደቡን ሳዉቅ ማንም
አልቀደመኝም፡፡ ባንቱ ከአዲስ አበባ በምን ያህል ርቀት ላይ እንደምትገኝ ሳይቀር ራሴ ከተማዋ ድረስ ሄጄ ለክቼዋለሁ። ምክንያቱም ራሴ ነኛ ወደ'ዚያ እንዲልከዉ ከባልቻ በፊት የነበረዉን የሲራክ፤ ኃላፊ
የወተወትሁት። እንደ ተባለዉም ጓዙን ጠቅልሎ ሄደልኝ፡፡ ነገር ግን
ሳምንት ያህል እንኳን ሳይቆይ፣ ግዳጁን እያቋረጠ ወደ አዲስ አበባ መለስ ቀለስ አበዛ፡፡ የኋላ ኋላ እንዲያዉም ከነጭራሹ አልሄድም ብሎ መቅረቱን
ሰምቼለታለሁ። እንዲችዉ ሲቅበጠበጥ ከራርሞ አሁን ግን አይቼዉ አላዉቅም።

በእርግጥ ግዳጁን ለማቋረጥም ምክንያቱ እኔ እንደ ሆንሁ አላጣሁትም።

“እህእ” ብለዉ ጎሮሯቸዉን ሲጠራርጉ ባነንሁ። ለካንስ የንስሐ አባቴ ከፊቴ ቆመዉ ኖሯል በትዝታ እንዲህ ጭልጥ ያልሁት? ወይ እኔ!

“ሐሳብ ገባሽሳ”

“እሸቴ ሲሉኝ ጊዜ...”

“ልትነግሪኝ የምትፈልጊዉ ነገር አለ ልበል፣ ስለ እሸቴ?”

“ሰሞኑን ድምፁ ለኔም ጠፍቶብኛል። የት እንዳለ ያዉቃሉ? ነግሮዎት ከሆነ”
👍271