አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
570 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
ረበችልኝ..ገና ሳየው ዘጋኝ
‹‹በቃኝ››
‹‹ምነው?››
‹‹አራበኝም..ገንፎ ብዙ ቅቤ ጭቅ ያለበት ጥግብ እስክል ነው የበላውት››አልኮት እንደ ቤተክርስቲያን ከበሮ የተወጠረውን ሆዴን ገልጬ እያስቃኘዋት
‹‹ይመኙሻል እኮ ጐበዝ ነች..እኔም የእሷ ገንፎ ናፍቆኛል››አለቺኝ ይመኙሻል ማት የአጐቴ ሚስት ነች‹‹የእሷን ገንፎ እኮ አይደለም የበላውት…. እነሱ ጋር ቁርስ ገንፎ ሳይሆን በሶ ነበር››
‹‹እና ታዲያ የት በላህ?››
‹‹ከአባዬ ጋር ሌላ ቦታ ሄደን ነው የበላነው›› የዚህን ጊዜ የእናቴ ጆሮ ለወሬ ሲቀሰር ታወቀኝ፡፡እኔ ደግሞ ለማወራው ወሬ ትኩረት ሲሰጡኝ ደስታዬ ይጨምራል የማውራት ሞራሌም ከገደብ ያልፋል
‹‹ሌላ ሴትዬ ማነች?››
‹‹ከእነ አጐቴ ቤት ወደታች በሚወስደው መንገድ ሀኪም ቤቱ ጋር ልትደርሺ ስትይ የሆነ ቀርከሀ አጥር ያለው ቤት የለም?››
‹‹አዎ አለ››
‹‹ከእሱ ቀጥሎ ደግሞ ኪወክስ ያለበት ቤት የለም?››
‹‹አዎ አለ››ጮክ ብላ በተሞጠጠ ትዕግስት
‹‹እዛ ቤት ፀዳለ የምትባል ሴት የለችም?››
‹‹አለች አልህ እኮ››አንቦረቀችብኝ….ግን እኮ አላላችኝም
እሷ ቤት ነው ገንፎ የበላነው እናቴ ተንጨረጨረች እናባዋ ሁሉ በዓይኖቾ ግጥም አለባት..እኔም በዛው ልክ ግራ ገባኝ… እስቲ የእኛ ገንፎ መብላት እሷን እንዴት ነው እንዲህ ሊበሳጫት የቻለው?ነው ወይስ ገንፎ ጥሩ አይደለም ሌላ ምግብ ለምን ሳታበላቸው ብላ ተናዳ ይሆን ?
‹‹ጥዋት ቁርስ ስለሆነ ነው እንጂ ማታ እኮ የሚጣፍጥ ዶሮ ወጥ… እንቁላል ስጋ ሁሉ ያለበት ነው የበላነው››
‹‹ይህቺ ናት እና ልጅት..ደግሳ ነዋ የጠበቀቻችሁ››
‹‹አዎ ደግ ሴት ነች ግን የሆነ ስጋ ላይ…››
‹‹እሺ የሆነ ስጋ ላይ ምን ሆነ?›.እናቴ ነች የወሬ ረሀቦ እያንቀጠቀጣት የጠየቀችኝ፡፡
‹‹ሁለቱ ብቻ እንደዚህ ከጫፍና ጫፍ ያዙና ጐትተው በመበጠስ ከተካፈሉ ብኃላ ለእኔ ሳይሰጡኝ ለራሷቸው ተጐራረሱ
‹‹መቋደሻም እስከመቋደስ ደርሰውልኛላ..የለውማ፡፡ እናትህን ነዋ ወስዶ ያስተዋወቀህ››
‹‹ኸረ እናቴ አይደለችም››ገና ለገና ለአንድ ቀን ዶሮ ወጥ እና ገንፎ ስላበላች እንዴት ነው አስናቴ የምትሆነው?››
‹‹ነች ባክህ››ብላኝ እቤቱን ጥላልኝ ወጣችና ወደ ጐሮ
የእናቴ የብስጭት መንስኤው ምንም ሊገባኝ አልቻለም…..ነው ወይስ ዶሮ ወጥ አምሮት ይሆን? ሴትዬዋን ለምኜት ይዤላት በመጣው ኖሮ… ብዬ ተቋጨው፡፡ ተነሳውና ወደ ጐሮ ተከተልኮት እያለቀሰች ነበር ፡፡ ሄድኩና ስሮ ቆምኩ ፈርቼያታለው..ትመታኛ ይሆን..?ብዬ ሳስብ ጭራሽ ወደ ራሷ ጐተተቺኝና ጉልበቶ ላይ አስተኝታኝ ፀጉሬን ታሻሽልኝ ጀመረ፡፡
‹‹ውሻዬ››
‹‹አቤት እማ››
‹‹ማታ ከማን ጋር ነው የተኛሀው …ፈራ ተባ እያለች በፍራቻ የጠየቀችኝ ጥያቄ እንደሆነ ያስታውቅባታል
‹‹ከነ ደጉ ጋር››መለስኩላት ደጉ ማለት እኩያዬ የሆነ የአጐቴ ልጅ ነው
‹‹አባትህስ?››
‹‹እሱ እኔ እንጃ የት እንዳደረ››
‹‹እንዴት?››
‹‹አላውቅማ… ማታ መጣው ብሎ ወጣና ቆየብኝ እኔ እንቅልፍ ወሰደኝ ፡፡ጥዋት ስነሳ እቤት የለም እና ፈለግኩትና ሳጣው እዛ ሴትዬዋ ጋር ሄድኩ.. አልጋዋ ላይ ቁጭ ብሎ ገንፎ ሲበላ ደረስኩ … ከዛ እኔም አብሬያቸው በላው››
ከዛ ኃላ እናቴ ፀጥ አለች፡፡ከተወሰነ ቆይታ ብኃላ ከተቀመጥንበት ተነሳንና ወደቤት ገባን..ትልቁን ሻንጣ አወጣችና የእሷን እና የእኔን ልብስ ብቻ እየመረጠች ትጠቀጥቅ ጀመር ….ግራ ገባኝ
‹‹እማ የት ልንሄድ ነው?››አልኮት
‹‹አያቶችህ ጋር››አለቺኝ ለስለስ ብላ..ደስ አለኝ በህይወቴ አያቶቼ ጋር እንደመሄድ የሚያስደስተኝ ነገር የለም
‹‹ግን ትምህርቴስ?››
‹‹አስፈቅድልሀለው›› ብላ አረጋጋችኝ
ሌላ የሚያሳስብ ሀሳብ ደግሞ በአዕምሮዬ መጣብኝ
‹‹አባዬስ ከእኛ ጋር ይሄዳል?››
‹‹ሁለታችን ብቻ ነን የምንሄደው››
‹‹ግን ምሳ ምናምን ማን ይሰራለታል?››
‹‹አይዞህ አታስብ አፀደ ጋር ሄዶ ይበላል››አለቺኝ
ሻንጣውን ጠቅጥቃ ዚፑን ዘጋግታ ከጨረሰች ቡኃላ ሻንጣውን ወደ በራፍ ጐትታ ለጉዞ እና ለነገር ዝግጁ ሆና አባቴን ትጠብቅ ጀመር፡፡
ቀጠዩ እና የመጨረሻው ምእራፍ ነገ ይቀጥላል
ብዙም ዛይቆይ አንድ የእናቴ ጓደኛ ወደ ቤታችን መጣች፡፡
‹‹ምን ሆነሽ ነው አይንሽ ያባበጠው?››እናቴን በማዳነቅ ጠየቀቻት
‹‹አይ ምንም አልሆንኩ…ዝም ብዬ ነው››
‹‹እንዴት ዝም ብለሽ ?አይንሽ እኮ ደም ለብሷል››
‹‹ቁጭ በይ ባክሽ›› አለቻት እናቴ ቆማ በጥያቄ ምታፋጥጣትን ጐደኛዋን…ልትቀመጥ ወደመቀመጫዋ ስትሄድ ዓይኖቾ ለጉዞ ዝግጁ የሆነው ሻንጣ ላይ አረፈ
‹‹እንዴ !!!ሻንጣ የት ለመሄድ?››
‹‹ወደቤተሰቦቼ ››
ኸሀ ገባኝ..ከባልሽ ጋር ተጣላቹ ማለት ነው?››
ዝም አለች እናቴ
‹‹ንገሪኝ እንጂ ምን ይዘጋሻል..ከእኔ ምን ምደብቂው ነገር አለሽ?››
‹‹ባክሽ ሰውዬው ፀዳለ ምትባል ሴት ወሽሞል አሉ››አለቻት…‹‹መወሸም ››ማለት ምን ማት ነው? አልገባኝም..ግን የሆነ መጥፎና የሚያናድድ ነገር እንደሆነ ገባኝ፡፡
‹‹ አትይኝም…ውይ ወንዶች!!!!›› ከእናቴ በላይ ተንዘረዘረች
‹‹ይሄውልሽ እንዲህ ተጫወተቨብኝ እልሻለው››
‹‹ለመሆኑ ካንቺ ምን አጣው ብሎ ነው?››አለቻት በከፍተኛ ማዳነቅ አፎን በእጆቾ አፍና
‹‹ያንቺስ ባል አንቺን ጥሎ ቤቱን እና ልጆቹን ጥሎ ሌላ አግብቶ የሄደው ካንቺ ምን አጥቶ ነው?››አናዳጅ ጥያቄዋን በአናዳጅ ጥያቄ መለሰችላት
‹‹እሱስ እውነትሽን ነው…ወንዶች ሲባሉ ያቺንም.. ያቺንም መልከፍ የሚወዱ ውሾች አይደሉ››
‹‹እና እንደዛው ነው››
‹‹እና ምን ልታደርጊ ነው?›.
‹‹በቃ ልጄን ይዤ ወደቤተሰቦቼ እሄዳለው….ከፈለገ ያምጣትና አብሮ ይኑር››
‹‹ጐበዝ..የታባቱ!!1 ይብላኝ ለእሱ እንጂ አንቺስ ደህና ቤተሰቦች አሉሽ..በዛ ላይ ገና ነሽ የፈለግሽውን ማግባት ትችያለሽ››አትል መሰላችሁ ስሬ ያለውን የውሀ ብርጭቆ አንስጬ ግንባሮን ብተረክክላት ደስ ይለኝ ነበር…እየሰማው አባቴን ‹ምናባቱ› ብላ ፊቴ ትሰድነበዋለች በጣም አናደደችኝ፡፡
‹‹አረ የምናባቱ ማግባት..ሁለታኛ…አርፌ ልጄን አሳድጋለው..ብቻ በሰላም ይልቀቀኝ እንጂ››
‹‹እሱማ ያው ሽማጊሌ ማንጋጋቱ አይቀርም››ቀጠለች ጐደኛ ተብዬዋ
‹‹…አይ እንዴት አንጀቴ እንዳረረ አታውቂም…. እንኮን የሰው ሽማግሌ ይቅርና እግዚያብሄርን ቢልክ አልሰማው፡፡ታውቂያለሽ አይል..ይሄ እኮ የመጀመሪያው አይደለም ከዚህ በፊትም ተመሳሳይ በደል በድሎኝ ለልጄ ስል ነበር በመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ይቅር ያልኩት አሁንማ እራስን ማስናቅና የእሱ መጫወቻ መሆን ነው..በሽታውን ተሸክሞብኝ መጥቶ ልጄን እንዳላሳደግ አጉል ቢያደርገኝስ?››
‹‹እና ጥዋት ልትሄጂ ነው?››
‹‹አዋ አሁንም መኪና አላገኝም እንጂ እዚህች ቤት ማደር አልፈልፈግም ነበር››
‹‹ይሁን እስቲ እኔም ሰሞኑን ስለምመጣ ጠይቅሻለው አይዞሽ በርቺ እንደእኔ ጥሎሽ ከመውጣቱ በፊት አንቺ ቀድመሽው ጥለሽው መውጣትሽ አሪፍ ነው››ብላ የውሳኔዋን ትክክለኝነት አረጋገጠችላት እና እናቴን አበረታታ እና ተሰናብታ ከቤት እንደወጣች እኔም ከኃላ ዋ ተከትዬት እቤቱን ለቅቄ ወጣው ነገ ወደ አያቶቼ መሄዴ ቁርጥ ጉዳይ ስለሆነ ጐደኞቼን ለመሰናበት…ስዞር ቆይቼ ሲጨልም ወደቤት ተመለስኩ አባቴ አልመጣም እናቴ ሰውነቴን አጥባ እራቴን አብልታኝ ‹‹ በለሊት ስለምንነሳ በጊዜ ተኛ›› ብላ አስተኛችኝ ረጅም ቀን አሰዋልፌ ስለነበር ወዲያው እንቅልፍ ወሰደኝ ስንት ሰዓት እንደሆነ አላውቅም በግምት ከለሊቱ 5 ወይም 6 ሰዓት ይሆን ይመስለኛል ሀይለኛ የበር መንጐጐት ከእንቅልፌ አባነነኝ
👍71
...እናቴ ሳያት ከመተኛቴ በፊት የተቀመጠችበት ቦታ እንደተቀመጠች ነው..እስከአሁን እንዳልተኛች በሁኔታዋ ያስታውቃል፡፡
‹‹አንቺ ሴትዬ አትሰሚም እንዴ?››የአባቴ ድምፅ ነው..ትንሽ ኮልተፍተፍ ብሎል፡፡ልከፍትለት ከአልጋዬ ስወርድ
‹‹አርፈህ ተኛ››ብላ አንቦረቀችብኝ..ከራማዬ ተገፈፈና ወደ መኝታዬ ተመለስኩ
‹‹ኸሀ… እየሰማሽ ነው ለካ..?ነው ወይስ ማልመጣ መስሎሽ ያስገባሽው ሰው አለ ?››
‹‹ሰው ሁሉ እንደአንተ ሸርሙጣ ይመስልሀል አይደለ?››ብለው እርፍ..ይ እንግዲህ ሰውን ቀና ብላ ማናገር እንኮን ከምትፈራው ከጭምቶ እናቴ የወጣ ዓረፍተ ነገር ነው
‹‹ሸርሙጣ…እኔ ሸርሙጥ?››ይሄንን በር ሳልገነጥለው ክፈቺ››አባቴ ድንፋታ መጠኑን ጨመረ
‹‹አልከፍትም..ትናንት ያሳደረችህን ጋር ሄደህ እደር››
በራፉን የተደረመሰ እስኪመስል ተነቃነቀ..እናቴ ተሸነፈችና በአቋሞ መፅናት አቅቶት የበራፉን መሸንጐሪያ ጐትታ አላቀቀችው..በር ወለል ብሎ ተበረገደ፡፡ አባቴም ተንደርድሮ ወደ ውስጥ እንደገባ መሀል ወለል ላይ የተገተረችውን እናቴን በጥፊ አላሳት..በርግጫ ደገማት..፡፡ በቅፅበት ቤቱ ቀውጢ ሆነ፤ እኔም እሪታዬን አስነካውት…የእሷን ጩኸት ማስቆም ሲያቅተው ወይም የእኔ ጩኸት ከእሷ ጩኸት በላይ ስለረበሸው ይመስለኛል ተንደርድሮ መጣና በዛ ሰፊድ እጁ አንዴ በጥፊ ሲያልሰኝ ፀጥ አልኩ ..በቃ ድዳ ሆንኩ፡፡እናቴ ግን ጭራሽ አበደች‹‹ልጄን አትንካው..እኔኑ እንደጀመርክ ጨርሰኝ….ይሄውልህ…››በዚህን ጊዜ ጐረቤቶቻችን ከየአቅጣጫው የጩኸት ድምፅ ሰምተው ይመስለኛል እየተሮሮጡ ሲመጡ ተሰማ…..ደርሰው ቤታችንን ደጃፍ አልፈው ወደ ውስጥ ገመዝለቃቸው በፊት አባቴ እየተንገዳገደ ሄዶ በራፉን ጠረቀመባቸው
እናቴ ‹‹አሳወጣኝ እዚህ ቤት አላድርም፣››ብትል ከውጭ ያሉት ሰዎች ‹‹በራፉን አንዴ ክፈትልን ››ብለው ቢማጸኑት..በራፉን ቢደበድቡ አንባገነኑ አባቴ ሊሰማቸው አልፈልግም፡፡ ቡኃላ እናቴ ተስፋ ስትቆርጥ መሰለኝ ጐረቤቶቾን‹‹ በቃ ወደ ቤታችሁ ግቡ… ብቻ ያደረገኝን ሁሉ በልቦናችሁ ይዙት ..ሞቼ ከተገኘውም እሱ እንደሆነ እወቁና ለዘመዶቼ ንገሩልኝ ሰላም ካደርኩ ነገ በህግ አንቀባርረዋለው..መንግስት ባለበት ሀገር እንዲህ አይጫወትብኝም..የሴቶች መፍት በተከበረበት ዘመን ላይ ነው ያለነው…››በማለት ከሰፊ መግለጫ ጋር እንዲሄዱ አደረገች፡፡ከዛ ቡኃላ ሲጨቃጨቁ ሲነታረኩ‹ ተኚ …አልተኛም፤ ልንካሽ …አትነካኝ› ሲባባሉ እኔ ሳዳምጥ ሳዳምጥ እነሱ ከመድከማቸው በፊት እኔ ዛልኩና እንቅልፍ ይዞኝ ጥግ አለ፡፡
…. ስባንን የጥዋት ፀሀይ በበራፋችን ስንጥቅ ወደ ቤት ገብቶ ሳሎናችንን አድምቆታል፡፡ አባቴ በጥፊ ያላሰኝ ፊቴ እየለበለበኝ ነው‹‹..እንዲህ አቃጥሎኝማ ሁለተኛ አላናግረውም ..አሁኑኑ ነው ጠዬው ወደ አያቴቶቼ ጋር እናቴን ተከትዬ የምሄደው…››በማለት ዓይኔን በመከራ ከፈትኩና ከአልጋዬ ወረድኩ..እናቴ ያሰናዳችው ሻንጣ እዛው በራፍ አካባቢ ዝግጁ እንደሆነ ነው
‹‹…እናቴ የት ሄደች..? እንዴት እስከአሁን አረፈደች…? በለሊት አልነበረ እንዴ እንሄዳለን ያለቺኝ?›› ግራ እንደተጋባው ዝም ብዬ ወደ ወላጆቼ መኝታ ቤት አመራው በራፉ አልተቀረቀረም ገርበብ እንዳለ ነው፡፡ገፋ አደረግኩና ወደ ውስጥ ገባው ጠላታችሁ ክው ይበል ክው ነው ያልኩት..ከዛን ቀን በፊት ሆነ ከዛ ቡኃላ በእንደዛ ዓይነት ሁኔታ ደንግጬ አላውቅም….ከወገብ በላይ ሁለቱም እርቃናቸውን ናቸው.. እቅፍቅፍ ብለው ከመጣበቃቸው የተነሳ ሁለት ጫንቅላት ያለው አንድ ሰው ነው የሚመስሉት፡፡የ ሁለቱም ልብስ ወለል ላይ ተዝረክርኮል፡፡በሁለቱም በጣም ተበሳጨው… በተለይ በእናቴ ፡፡አስጠሉኝ ፡፡ተመልሼ ወደ ሳሎን ገባው የእናቴን የገንዘብ ቦርሳ ጠረጵዛ ላይ አየውት… ከፈትኩት እና ከውስጡ የተወሰነ ብር ዛቅ አድርጌ ኪሴ ከተትኩ፡፡እናቴ ስትፎክርበት እና ስታስፈራራበት ያመሸችውን ትልቅ ሻንጣ ከፈትኩና ከውስጡ ራሴን ልብሶች መርጬ በትንሽ ፔስታል ጨመርኩና የሳሎኑን በር ከፍቼ ቤታቸውን ለቅቄላቸው ወጠው ፡፡ወደ መነኸሪያ..ሁለቱም ናቸው ያስጠሉኝ፡፡ እነደዛ ለእሷ ስል በጥፊ ተቃጥዬ ጭራሽ አቅፋው ትተኛለች..?ኸረ ከእነዚህ ጋር ማን ይኖራል…? አያቶቼ ይሻሉኛል፡፡

💫አለቀ💫

Like 👍እየቀነሰ ነው አትቆጥቡ😜
👍 እያረጋቹ

አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን
👍8😁4
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_ሁለት
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

...ኢትዬጵያን በዩቶፐያ ፅንሰ ሀሳብ ዳግም መገንባት ከአያቴ የወረስኩት ህልሜ እና ዓላማዬ እንደሆነ ነግሬያችኃለው …ግን እንዴት አድርጌ ነው የማሳካው …?እንደማሳክው የማምነው ከራሴ በላይ በሚስቴ እምነት ስላለኝ ነው፡፡ሚስቴ …የዋናው የታሪኬ ማጠንጠኛ እሷ ነች፡፡እሷ ደግሞ መንፈስ ነች፡፡ገራሚ መንፈስ፡፡አስፈሪ መንፈስ፤ታሪካዊ መንፈስ፤አፍዛዥ መንፈስ…ሁሉን አድራጊ ፈላጭ ቆራጭ መንፈስ፡፡አዎ ስለእሷ የምነግራችሁ ነገር ቢኖር የደረስኩበትን እና ያወቅኩትን ብቻ ነው፡፡ያንን ስላችሁ በቃ ስለእሷ የማትነግረን ጥቂት ነዋ..?››ብላችሁ ታስቡ ይሆናል፡፡አይደለም:: እንደውም በተቀራኒው የምነግራችሁ ከእሷ ታሪክ አንጻር ጥቂቱን ግን በእኛ በሰውኛ ልኬት ከጆሮአችን የመስማት አቅም በላይ ከአይኖቻችንም የማየት ጉልበት በላይ በሆነ መጠን ነግራችሆለው፡፡
ምክንቱም ይህቺ ፍቅሬ ከሰፈር ጎረምሳነት በአንዴ ስለዓለም መፅአዊ እጣ ሚያስብና ለዛም የሚሰራ የሚተጋ ሰው አድርጋ መልሳ ዳግመኛ የፈጠረቺኝ ሴት ነች፡፡እሷ ደፋርም ገራሚም ፍጡር ነች፡፡ ሁሉ ነገር የማድረግ አቅም እንዳላት አምናለው፡እንዴት አድርጌ የምታደርገው ነገር ሁሉ የምትለውን ሁሉ አምናታለው፡፡የማምናት ጅል ሆኜ አይደልም፡፡በአፍቃሪነቴም ዓየነ-ልቦናይ ታውሮም አይመስለኝም፤የምትሰራቸውን የእጆቾን ተአምራቶች በአይኖቼ ደጋግሜ ሳላየው ላለማመን አልችልም፡፡ ግን ደግሞ ሚስጥሯን ሁሉ ትነግረኛለች ብዬ አላስብም…ከእኔ የተደበቀ የሆነ ዕቅድ ያላት መስሎ ይሰማኛል ፡፡ቢሆንም ደፍሬ ጠይቄያት አላውቅም፡፡
ግን የምታወራው ስለአፈቀርካት ሴት ነው ወይ..? ካላችሁኝ አዎ ስለእሷው ነው፤ግን እንደምታውቋት አይነት ሴት ብቻ አይደለችም… መንፈስም ጭምር ነች፡፡ምን አይነት መንፈስ..?እሱን ወደ ፊት አስረዳችሆለው….
ይህቺን ሴት ያገኘዋት በተለየ አጋጣሚ ነው፡፡በህይወቴ የመጨረሸውን ሀዘን ባዘንኩበት ቀን …የመጨረሻውን እጦት ባጣውበት ቀን…ወደ ልቤ ደም የሚወስዱና የሚመልሱ ትላልቅ የደም ስሮች የተበጠሱ የመሰለኝ ቀን፡፡አዎ የዛን ቀን ነበር ያገኘዋት …፡፡እንዴት እጦቴን በተአምሮ መለሰችልኝ…ሀዘኔን በድንቅ ስራዋ ወደምስራች ቀየረችልኝ…የተበጣጠሱትን የልብን ደም ስሮች ቀጣጥላ ለሞት ከቆረጥኩበት ስሜት አውጥታ መኖርን እንድናፍቅ አደረገቺኝ እና በዛኑ ቅፅበት ይህቺን ሴት ደነዘዝኩላት….፡፡
ወዲያው ነበር እግሯ ስር ተንበርክኬ እንዳፈቀርኳት የነገርኳት..ይቺን ሴት ፍቅሬን እንደተቀበለች ነበር ትንፋሽ ሳልሰጣት እንድታገባኝ የጠየቀኳት፡፡አግቢኝ ስላት ቤት አልነበረኝም .አግቢኝ ስላት ስራ አልነበረኝም…አረ አግቢኝ ስላት የሀይስኩል ትምህርቴን እንኳን አልጨረስኩም…አግቢኝ ስላት የማግባት ዕቅድም አልነበረኝም….አግቢኝ ስላት ዕድሜዬ እንኳን 18 ሊደፍን ገና 3 ወራቶች ይቀሩት ነበር..
ይህ ሁሉ ቢሆንም ዳሩ እንድታገባኝ ስጠይቃት
-እንዳገባህ የጠየቅከኝ ውለታ ስለዋልኩልህ ነው ወይስ ስላፈቀርከኝ›ነበር ያለቺኝ
-ሁለቱም ምክንያት ነው፡፡-መለስኩላት
-ይሁን የመጣውትም አንተን ለማግባት ስለሆነ ተቀብዬሀለው ››አለቺኝ
-አልገባኝ
-ቀስ ብሎ ይገባሀል ..ለማንኛውም ጥያቄህን ተቀብያለው ፡፡አገባሀለው፡፡
መልሶን ስሰማ ደንግጬ ነበር..እሺታዋን ስሰማ ፈዝዤ ነበር፡፡አዎ እሺታዋን አልጠበቅኩም ነበር፡፡
-ግን ቆይ የመጣውት ስትይ ከየት ነው የመጣሽው.?
ከዛኛው አለም ….ላለፈት መቶ አመት እዚህ አልነበርኩም፡፡
-ያው እየቀለደች ነው ብዬ
‹ከዛ በፊትስ?፡›ጠየቅኳት
-ከዛ በፊት አንድ አራት ጊዜ ተመላልሺያለው፡፡ፈርዶብኝ ጀግና ወዳለው፡፡በዚህ አካባቢ ማለቴ በኢትዬጵያ ጀግና መኖሩን ከሰማው በርሬ ለመምጣት ቀናትን አላባክንም›
-ይገርማል…አሁን ታዲያ ማን ተገኝቶ ነው የመጣሺው.?›
-ነገርኩህ አንተን..
-እኔን …እኔ ታዲያ እንዴት ነው ከሌላ አለም የሚመጣልኝ ጀግና የሆንኩት?››ጠየቅኳት ያው በቀልድ ቅላፄ
-አይ እስከአሁን እንኳን ጀግና አይደለህም ….ግን ጀግና የሚሆን ልብ ይዘሀል፡፡በሺ አመት አንዴ የሚገኝ ጀግና ልብ…ስለዚህ አገባሀለው፡፡ግን አንድ አላማ አለኝ ያንን እንዳሳካ ታግዘኛለህ …እርግጥ ለእኔም ብቻ ሳይሆን ለአንተም ይጠቅማል፡፡
-አረ ግድ የለም ፡፡ለአንቺ ብቻ የሚጠቅምም ቢሆን ያልሺኝን ሁሉ አደርገዋለው›አልኳት ከልቤ እንደማደርገው በውስጤ እየማልኩ
የእለቱ ንግግራችንም ሆነ ጠቅላላ ታሪኩ በዚህ አልተቆጨም ሙሉውን ወደፊት አወራችሆለው …አሁን ከዚያች የህይወት አጋጣሚ አክለፍልፋ ወስዳ እሷ እጅ ወይም ልብ ላይ እስክትጥለኝ ድረስ ያሰለፍኩትን የእኔንና የቤተሰቤን ታሪክ ልክ እንደቅምሻ በሚቀጥሉት ክፍል አወራችሁና ስጨርስ ወደመነሻዬ እመልሳችሆለው፡፡

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3
#አስራ_ሶስተኛው_ፍቅር !

እንዴት ዋላችሁ ህዝቤ? ሁሉ ፒስ ነው ወይ? በቃ ምንም እንደሌለብህ ሐገርህን ለአክቲቪስት ጥለህ ለጥ ትልልኛለህ ኣ? ለነገሩ ለምን ይዋሻል እኔም በጥልቅ እንቅልፍ ውስጥ ሆኜ ነው ያደርኩት! ህልሜን ሁሉ በሪሞት እየቀያየርኩ ሳይ ነበር። “ደሃ በህልሙ ቅቤ ባይጠጣ ኖሮ” .... አሉ አበው (መቼስ የኛ ሐገር አበውና የኛ ሐገር አክቲቪስት ማይለው የለም) የምር ግን እኛ ድሆች በህልማችን ቅቤ ባንጠጣ ኖሮኮ ...... ያው አልጠጣንም ነዋ ምናባታችን እናመጣለን!😄
እና በተረፈ ሁሉ አማን ነው ወይ? እኔ ለአስራሶስተኛ ግዜ ፍቅር ይዞኝ መከራዬን ሳይ ነው የከረምኩት። ያው እንደህንድ አክተር ፍቅር ሚያጠቃኝ ነገር አለ ኣ?? .... ልቤ ተላላ ነገር ነው። ከአንድ ሴት ጋር ተግባብቼ ትንሽ ከተጨዋወትኩ ጠላታችሁ ቅይር ይበል ቅይር እላለሁ። ፈገግታዋ ልቤን ትርክክ ያደርገዋል። ሰባት ግዜ የሰማሁትን ቀልድ ስትነግረኝ እየተንፈራፈርኩ እስቃለሁ። አረ ስተኛ ራሱ በህልሜ አያታለሁ። ይኸው እኛ መስሪያቤት የምትሰራው ትርሲትም ሰው ነው ብላ ብትቀርበኝ አፍቅሪያት አረፍኩት! ባፈቀርኳት ማግስትም የናቲ ማንን «የመጀመሪያዬ ነው ሰው ስወድ አምርሬ» የሚለውን ዘፈን ጋበዝኳት! (በርግጥ «አስራሶስተኛዬ ነው ሰው ስወድ አምርሬ» አይባል ነገር ችግር ሆኖብኝ እንጂ የመጀመሪያዬንኳ አልነበረም!)
ከትርሲት ጋር ብዙ ግዜ አብረን ብንሰራም በፍቅር አይን አይቻት አላውቅም ነበር። ባለፈው የአንድ የስራ ባልደረባችን እናት ድንገት አረፉና ማታ ከመስሪያ ቤታችን ሰዎች ጋር ለቅሶ ቤት ሄድን።
ድንኳኗ በሰው ተሞልታለች። ወጣቶቹ በካርታ ቁማር እየተጫወቱ ድንኳኑን ካሲኖ አስመስለውታል። በሩ አካባቢ ቁጭ አልን። ያው እኔ አርፌ አልቀመጥም አይደል አይኔን ማንከራተት ጀመርኩ። እናንተ!! ሰዉ ይሄን ንፍሮ ይዝቀው የለ እንዴ? ጥግ አካባቢ ያለው ሰውዬማ ንፍሮውን ከሰሃኑ እየዘገነ በሁለቱም የጃኬቱ ኪስ ውስጥ ጠቅጥቆ ብድግ ሲል ቦንብ የታጠቀ ነበር የመሰለኝ።
ትንሽ እንደቆየን አንዱ ሰካራም ገድገድ እያለ ከውጪ ገብቶ ወደኛ ጠጋ አለና
«ጋሽ ለገሰ ሞቱንዴ?» አለን
«አይ የጋሽ ለገሰ ለቅሶ አይደለም» አልነው።
«አሃ አሃ! ለካ እሳቸው አምና ሞተዋል። ፊት ለፊት ያለው ግቢ የሚኖሩት መምህር ጥበቡ ነዋ የሞቱት» ሲል
«አረ ኔ አለሁ ምን ያሟርትብኛል ይሄ» አሉ ከኋላችን የተቀመጡ ሰውዬ።
በወሬው የተሰላቸው ሰካራም «በቃ ማንም ይሁን ማን የሆነ ሰው ሞቷል። ዋናው ጥያቄ እራት ሰአት አልፏል ወይ? የሚለው ነው» ሲለን ሳቃችንን እንደምንም ተቆጣጥረን ጠጋ ብለን አጠገባችን አስቀመጥነው።
ትንሽ ቆይቶ ራት ቀረበ። ፒፕሉ የተቆረጠውን እንጀራ እንደቆሎ ዘገነው። ሰውዬውም እንጀራውን እንደአንሶላ ደራርቦ ሰሃኑ ላይ ካነጠፈ በኋላ ወጥ አስደርጎ ከራሱ ጋር እየተሻማ ሁለት ሶስቴ ጎረሰና ረሃቡ መለስ ሲልለት ወደኔ ዞሮ
«ምን ሆነው ሞቱ ግን?» አለኝ
«መኪና ገጭቷቸው መሰለኝ» አልኩት። ከልቡ አልሰማኝም እንጀራውን እየጠቀለለ
«እና ተረፉ?» አለኝ
«እንዴት ተረፉ?» አልኩት ግራ ገብቶኝ
«ውይ የኔ ነገር ሞተዋል ለካ ... ባክህ ስሞትልህ አንዴ ላጉርስህ» አለኝ እንጀራውን ወደአፌ እያስጠጋ
«አይ በልቻለሁ ይቅርብኝ» ስለው «ይሁና» ብሎ ምግቡን ጨርሶ ከበላ በኋላ ከመቀመጫው ተነሳና ባርኔጣውን ከፍ አርጎ
«ያመት አመት ሰው ይበለን። መጥተን አንጣችሁ» ብሎ ወጣ።
በሰውዬው ሁኔታ እየሳቅን ሳለ ነው ትርሲት ከተፍ ያለችው! እግዚኦ ውበት! እግዞኦ ቁንጅና! ሰው ለቅሶ ቤት ለመምጣት እንዲህ ይሽቀረቀራል በናታችሁ? መስሪያ ቤት የማውቃት ትርሲት አትመስልም። ያቺን ትርሲት እዛው መስሪያቤት አወላልቃ ጥላ አዲስ ታጥቦ የተተኮሰ ቆዳ ለብሳ የመጣች ነው ምትመስለው። መስሪያ ቤት ጠቅልላ የምትቋጥረው ፀጉሯ ራሱ ተለቆ ትከሻዋ ላይ እየተዘናፈለ ልዩ ውበት ሰጥቷታል (ያው የራሷ መሆንና አለመሆኑ በሂደት ይጣራል) አንገቷን እንዳቀረቀረች ወደድንኳኑ ገብታ ተቀመጠች።
«እቺን ልጅ እስካሁን እንዴት አላፈቀርኳትም» አልኩ በልቤ። አንዳንዴኮ አይጋርድባችሁ ወንድሞቼ!
ከለቅሶ ቤቱ ስትወጣ ተከትያት ወጥቼ ሸኘኋት። በቃ ከዛን ቀን ወዲህ ተቀራረብን። በየቀኑ መገናኘት ጀመርን። ሻይ ቡናም ተባባልን። አረ እራትም በልተናል። በርግጥ እራት በላን ከምል ማጅራት ተመታሁ ብል ይቀለኛል።
ማውቀው ቤት አለ ብላኝ የከተማዋ ቱጃሮች ሚዝናኑበት ባር እየጎተተች ይዛኝ ሄደች።
የባሩ ዋቴ የጀመረው ገና ስንገባ ነው። ጋርዱ ጠብ እርግፍ ብሎ እጅ ነስቶ በር ከፍቶ በትህትና ሲያስገባኝ ነው መፍራት የጀመርኩት። ልክ ገብተን እንደተቀመጥን አስተናጋጇ ወርቃማ ፍሬም የሚመስል ሜኑ አመጣች። ትርሲት ልክ ማትሪክ እንደሚፈተን ሰው ሜኑውን በጥሞና ስታነብ ቆይታ የሆነ ምግብ አዘዘች። እኔም አይኖቿን እያየሁ ፈዝዤ እሷ ያዘዘችውን አምጪልኝ አልኩ። ከአፍታ ቆይታ በኋላ በሁለት ሰሃን ባቄላ ቲማቲም ምናምን ቀረበልን። ስታርተር መስሎኝ ዋናውን ምግብ ስጠብቅ ቀረ። ቢቸግረኝ ባቄላዬን በላሁና ሚጠጣ ለማዘዝ ቀና ስል አስተናጋጇ አጠገቤ ደርሳ «ምን ይጨመር የኔ ጌታ» አለችኝ። አስተናጋጇ ቤቱን ለማየትም እድል አትሰጥም። ቀና ባልኩ ቁጥር ተፈናጥራ እየመጣች «ምን ይጨመር» ስትለኝ ነው ያመሸችው። ዋይን በግላስ አዘዝኩ። ትርሲትም ነጭ ዋይን አለች። ብቻ ላሳጥረውና ቢሉ መጥቶ የወር ደሞዜን ዱቅ አርጌ ያን ምሽት እንዳኮረፍኩ ብዙም ሳናወራ ተለያየን።
ትርሲት ሁሉ ነገሯ ጥሩ ነው። እሷን ማፍቀሬም የሚካድ አይደለም። ግን ችግር አለ! በጣም ጨምላቃ ነች! ፍላጎቷ ከኔ አቅም በላይ ነው። ፋይፍ ስታር ሆቴል ካልሄደች እህል አይወርድላትም። አራት ዲጂት ያለው ቢል ካልመጣ የተዝናናች አይመስላትም። ሳስበው የቀድሞ ቦይፍሬንዷ ከሜቴክ ጋር ግንኙነት ሳይኖረው አይቀርም። መርከብ የበላ እንጂ እንደኔ አይነት ሚጢጢ ደሞዝ ሚበላ ሰው አይችላትም። በቃ ሁሉ ነገሯ ወጪ አለው። አንዳንዴማ የነዳጅ ጉድጓድ ያለኝ ሁሉ ሳይመስላት አይቀርም።
ፍቅርኮ ደስ የሚለው እንደአማርኛ ፊልም ቆሎ እየቆረጠሙ በሻይ እያወራረዱ፣ በቆሎ እየጋጡ ወክ ሲያደርጉ ምናምን ነው። እቺኮ ከእንትን ባር ወደእንትና ላውንጅ ነው። ከእንትና ላውንጅ ወደእንትና ስፓ ነው። ሁሉ ነገሯ ኤክስፔንሲቭ!
ቁጭ ብዬ የወደፊት ሂወቴን ከሷ ጋር ማሰብ ጀመርኩ። ምርጫዬ ሁለት ነው። ወይ ባንክ መዝረፍ ወይ ፍቅር ምናምን ሚባለውን ነገር እርግፍ አርጎ መተው! ድህነቴን እንደዘንድሮ ጠልቼው አላውቅም። ሟቹ ጠቅላያችን “ትልቁ ጠላታችን ድህነት ነው” ያሉት ራሱ እንደኔ አይነቷ ገጥማቸው ሳይሆን አይቀርም! .... ትርሲትን መተው ከባድ ነው። ባንክ መዝረፉም ቀላል አይደለም። ይሄኔኮ «ምን ጣጣ አለው ሰው አስራስምንት ባንክ ይዘርፍ የለንዴ» ትዪ ይሆናል አዳሜ። (ወዳጄ አንድ ቡድንኮ ከሶስት ግዜ በላይ ባንክ ከዘረፈ ከስተመር ነው እንጂ ዘራፊ አይባልም። እንደውም ባንኩ ቆጥሮ አስፈርሞ “አትጥፋ በሰላም ግባ” ምናምን ብሎ ነው ሚሸኘው)
በቃ ተሸበለልኩ! ነፋስ ሆንኩ! በኪሎሜትር እራቅኋት!
«አቅምን አውቆ መኖር ጥሩ ነው» ብሎ የዘፈነው ሰዉዬ ማን ነበር? ....ብቻ ማንም ይሁን ማን አፈላልጋችሁ የክብር ዶክትሬት ስጡልኝ!😂

🔘ዘውዳለም ታደሠ🔘
👍5😁1
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_ሶስት
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
....እናቴ ማለት….፨
ለእናቴ ያለኝ እይታ አምልኮ ደረጃ የደረሰ ዓይነት ነወ ፡፡ይሄን ቃል ስናገር በአላዋቂነት ስሜት ልቤን በትዕቢት አጨልሜ አይደለም፤በፍጽም ወይን
ም በእግዜያብሄር የፈጣሪነት ስልጣን ላይ እምነቴ የላላም ስለሆነም አይደለም፡፡አዎ ብቻ እንደዛ ማለት ስላለብኝ ነው፡፡እውነትም ስለሆነ ነው፡፡
የምፈራው እሷን ብቻ ነው፡፡የምሰማውም እንደዛው ፡፡እናቴን በአምስቱም የስሜት ህዋሳቶች ስጠቀም የመጨረሻውን ስሜት የማጣጥምባት ቅዱስ ጨረቃዬ ነች፡፡አፍንጫዬን ተጠቅሜ የመጨረሻው መሳጭ ሽታ ወደውስጤ የምምገው የእናቴን ጠረን ነው፡፡:በምላሴ ቀምሼ የምደነዝዛበት የመጫረሻው ጣፍጭ ጣዕም የእናቴ እጅ የነካው ምግብ ነው፡፡አይኖቼ ሲከፈቱ ሊመለከቷቸው የሚጓጉት የመጨረሻው መሳጭ ውበት የእናቴ ማንነት ነው፡፡በእጆቼ ሲዳሰሱ ስሜት የሚሰጡኝ ልቤን የሚያደነዝዘው የመጨረሻው ለስላሳ ልብ ነዛሪ ገላ የእናቴ ሰውነት ነው፡፡የመጨረሻው የሰማይ መላዕክት የሚደመሙበት አይነት ከያሬድ ዝማሬ የላቀው ጥኡመ ዜማ ከእናቴ አንደበት የሚወጣው ድምጽ ነው፡፡
እርግጥ ይሄ ስለእናቴ ያለኝ ስሜት የእኔ የተዛባ አመለካከት ሊሆነው ይችላል፤ቢሆንም ግድ የለኝም ፡፡እንደውም ይሄንን ስሜት ከውስጤ የሚያጠፋብኝን ጤንነት አልፈልገውም፡፡ለእኔ ዓለም ጠቅላላ ማለት እሷ ነች፡፡እሷ ብቻ ነች፡፡እሷ ብቻ ነች የምታወደኝ፡፡እሷ ብቻ ነች የምትኮራብኝ፡፡እሷ ብቻ ነች ውስጤን አንብባ ነገዬን በድፍረት የምትነግረኝ፡፡እሷ ብቻ ነች ያላትን በጠቅላላ ያለመሰሰት ልትሰጠኝ የማታንገራግር፡፡አሁን እርግጥ ከእናቴ በተጨማሪ ይህች አለም ሌላ እውነት እንዳለት ተረድቼያለው፡፡ሚስቴ …..
እናቴ ወላጄ ነች፡፡ከማይታወቀው አለም ለእናቶች ከእግዚያብሄር በተሰጠ የተፈጥሮዊ ፀጋ በመጠቀም ከሚስጥራዊው ዓለም መዛ አምጥታኝ በቅዱስ ማህፀኖ ዘጠኝ ወር ተንከባክባ ከረቂቅ ህዋስነት ወደ ሰዋዊ ፍጡርነት በመቀየር በሚዳሰሰው ዓለም ላይ እንድኖር ያደረገቺኝ እናቴ፡፡
አንድ ሴት ወደ ማህፀኗ ከገብት 5 ሚሊዬን በላይ የዘር ፍሬዎች መካከል አንዶ እድለኛ በሰበረችው እንቁላል ልጅ ይወለዳል፡፡እንዴት እኔ እንደዛ እድለኛ ሆንኩ..….?እንዴት ከአምሰት ሚሊዬን አንዶ እኔን የያዘች ሴል ተሳካላት…….?እዚህ ላይ የእናቴ አስተዋፅኦ ይኖርበት ይሆን ወይስ የፈጣሪ ፍቃድ….?፡፡የፈጣሪስ ከሆነ ምንድ ነው ምክንያቱ….? ምንድነውስ መስፈርቱ …….?፡፡
ለማንኛውም ይሄን ለጊዜው ልተወው…እናቴ ወደዚህ ምድር አመጣችኝ..ማለት ወለደቺኝ፡፡ይሄ ማኛውም እናት በእውቀትም ሆነ በደመነፍስ የምታደርገው ነገር ነው፡፡የእናቴ ብቃት፤የእናቴ ልዩ መሆን፤የእናቴ ፈጣሪነት ከዛ ቡኃላ የሚገለጽ ነው፡፡መጀመሪያ ወለደቺኝ ከዛ ቀጥላ ፈጠረቺኝ፡፡ቅደም ተከተሉ አዛባውባችሁ አይደል….?፡፡መፈጠር የነገር ሁሉ መጀመሪያ እንደሆነ ስቼው አይደለም፡፡ እናቴ ስትወልደኝ እንደማንኛውም ሰው ሰው ነበርኩ፡፡ግን ዝም ብሎ ስው፡፡እየዳህኩ ሰሄድ ምኔም ምኔም የማይጥም ሰው ነበርኩ፡፡
እራሴን ላስተዋውቃችሁ አይደል፡፡እራስን ማስተዋወቅ እንዴት ነበር.. ….?አዎ ሰዎች እራሳቸውን ማስተዋወቅ የሚጀምሩት ስማቸውን ከመናገር አይደል ….?፡፡ሰው እራስ ወዳድ የመሆኑን አንዱ ማስረጃ ይሄ ነው፡፡ በየምክንያቱ ስሙን መጥራት ስለሚወድ እራሱን ለሌላ እንግዳ ስው የማስተዋወቅ ስርአት ላይ ስምን ቅድሚያ መናገር የሚል ሀረግ አሰፈረ……፡፡
ማህሌት ትባላለች፡፡ማህሌት ገዳ፡፡የእናቴን ሙሉ ስም እየነገርኮችሁ ነው፡፡የእኔ ስም ደግሞ ፀጋ ፡፡ፀጋ ማህሌት ገዳ፡፡ሙሉ ስሜ እስከአያቴ ሲጠራ ነው፡፡የሴት ልጅ ነኝ፤ ለዛ ነው በእናቴ የምጠራው፡፡አባቴን አላውቀውም..እንዳለኝ እንኳን እርግጠኛ አይደለውም፡፡እንዲኖረኝም ፈልጌም ጠብቄም አላውቅም ፡፡የተወለድኩት በ1994 ዓ.ምህረት ነው፡፡ስንት ዓመቴ እንደሆነ ቆጥራችሁ ድረሱበት፡፡እጆቼን ከመሬት አላቅቄ በአየር ላይ በማወናጨፍ ፤በሁለት እግሮቼ ቆሜ ሰው እንደሚያደርገው መራመድ የቻልኩት አራት አመት ካለፈኝ ቡኃላ ነው፡፡ከዛ በፊት ልክ እንደዝንጀሮ ወይም ጦጣ ወይንም ደግሞ እንደተሳቢ እንስሳት ባለአራት እግር ተሳቢ ወይም ተንፎቃቂ ነበርኩ፡፡
እናቴ በዛን ወቅት በተለይ ሁለት ዓመት ካለፈኝ ቡኃላ መራመድ ባለመቻሌ በጣም ተጨንቃ የተለያዩ ቦታ በመውሰድ ዘመናዊውንም ሆነ ባህላዊውን ህክምና እንዳገኝ እና እንደሌሎች እኩዬቼ መራመድና መናገር እንድችል ሞክራ ነበር ፡፡ግን አንዳቸውም ምንም ሊፈይዱልኝ አልቻሉም ነበር፡፡በመጨረሻ እናቴ ተጨንቃ እኔን ማስጨነቁን ለማቆም ከወሰነችና እሰከማንነቴ ልትቀበለኝ ከቆረጠች ቡኃላ ነበር ድንገት ተስፈንጥሬ በመቆም መሄድ የቻልኩት፡፡እንዴት መራመድ ቻልኩ ታሪኩ እንዲህ ነው፡፡

💫ይቀጥላል💫

Like 👍 እያረጋቹ አደለም ያነበበ የተመቸው 👍
እያረጋቹ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3
#የሰፋ_ሀገር_ይዘን_ጠቦ_መሞት_ይብቃን

አይችለው የለ እንጂ የልባም ትከሻ፣
ከውርደቱ ደጃፍ ነውሩን ማምለጥ ሲሻ፣
ገርፎ ማሳመን ነው የፈሪ ሰው በትር የሽንታም ሰው ጋሻ።
እንመን ግድ የለም…
ፍትህ አይታለምም ሀቁን እየሸሹ፣
የጠፋው እንዲገኝ እስኪ መጀመርያ ይፈተሽ ፈታሹ።
አቀርቅራ ታዝግም ትጎናበስ እንጂ መሄድ እስኪያድላት፣
ሰብረህ ስታበቃ ምርኩዝ እንኪ ብለህ ደርሰህ አትደልላት።
በኔ ብቻ በሽታ ጥበት እየቀጣን፣
በእናታችን እርስት በአባታችን መሬት መደገፊያ እያጣን፣
ቁልቁል እያሰቡ ምንድነው ከፍታ፣
መብት እየነጠቁ ምንድነው ግዴታ?
እስከ መቼ ተረት ግዴለም ይነጋል፣
መንገድ እየቀሙ ምርኩዝ ምን ያደርጋል?
አንተ እንደው ልማድህ አለስልሶ መግደል አሳስቆ
መግፋት፣
ካብኩ እያሉ ማቅለል ሳምኩ እያሉ መትፋት፣
የበደል ላይ ጀግና እሬሳ ላይ መዛት፣
መዋረድን ሽሽት የአሽቃባጭ አፍ መግዛት።
እየሸሹ ትግል እየሮጡ ዛቻ፣
በጉንዳን ልቦና የነብር ዘመቻ።
የበላ እያሰረ የቀማ ቢገፈው፣
የሳተ እያረመ ያጠፋ ቢገርፈው፣
ጀግና ልማዱ ነው ባርያ ሆኖ ታሽቶ ንጉስ ሆኖ መግዛት፣
እያነሰ ገዝፎ እየሞተ መብዛት።
ያ ሽንታም ላመሉ በሬሳ ይፎክራል፣
ከፈሪ ገዳይ ድል የጀግና ሞት ያምራል።
ይልቅ……
በእኔ ልቅደም ትርክት የዘር ደዌ አያጥቃን፣
ከጎጥ ቀንበር ፍቱን ጠቦ መሞት በቃን።
የጸደይ ወይን ሆኖ የሀቅ እንባ ቢጥም፣
በድሎ መጀገን ጀብድ ሆኖ ቢረግጥም፣
የትግላችን ልኩ ያሳር ደም ቢያስምጥም፣
በሰፋ ሀገር ጠበን ኢትዮጵያን አንሰጥም!!!

🔘ገጣሚ ህሊና ደሳለኝ🔘
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_አራት
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
አራት አመት ካለፈኝ ቡኃላ አንድ ቀን አናቴ ከጓደኛዋ ጋር የገዛ ቤታችን ውስጥ ታወራለች
‹‹እንደው ስንቱ እያፈቀረሽ እኮ ሁኔታሽን እያየ ነው የሚሸሸሽ››ድንገት ነው ጓደኛዋ አስተያየት የሰነዘረችው
-ሁኔታዬ ምን ሆነ ?
-ያው የልጅሽ ሁኔታ ነዋ
-የልጄ ሁኔታ ምን ሆነ..?በቃ በማንም ሰው ላይ እንደሚያጋጥም የጤና መጓደል አራት አመት ቢሆነውም መናገርና መራመድ አልቻለም..እና ምን ይጠበስ …….?በንዴት እና በሚርገበገብ ድምፅ
-ቀስ በይ ምን ያስቆጣሻል…ለማለት የፈለኩት ሙሉ ህይወትሽን ለእሱ መስዋዕት አድርገሽ ሰጥተሸል ነው፡፡ልጅሽ ቢሆንም አንቺም ሰው ነሽና ለራስሽ ማሰብ መጀመር አለብሽ ልልሽ ፈልጌ ነው….ቀንም ሌትም ከእሱ ጋር ተቆራምደሽ መዋልና ማደሩን አቁሚና ለሰራተኛ ሰጥተሸው እንደድሮሽ ወጣ ወጣ በይ….ወደቢሮ ስራሽም ተመለሺ እያልኩሽ ነው፡፡
-እኔ ወንድ ያስፈልገኛል ብዬ ለማንም ተናግሬ አላውቅም፡፡ወንድ ለማግኘት ከእኔ በስተቀር ሌላ ሰው ሊረዳው የማይችለውን ልጄን ለሰራተኛ ጥዬ ተቆነጃጅቼ ለመውጣት ፍላጎቱ የለኝም፡፡ለምበላውና ለምጠጣው የሚሆን ብር አለኝ፡፡ስለዚህ አትልፊ ከአሁን ቡኃላ ባለው ህይወቴ ዋና አላማዬም ሆነ ቋሚ ስራዬ ልጄ ነው፡፡…እናቴ ፍርጥም ያለ መልስ ትመልስላታለች፡፡
-አይ ተስፋ ለሌለው ነገር እራስሽን መስዋዕት እንድታደርጊ ስለማልፈልግ ነው እንደዚህ የምልሽ..ደግሞ ለአባትሽም ብታስቢላቸው መልካም ነው::
እዚህ ላይ እናቴ ብትበሳጭም የጓደኛው ምክር ግን እንዲሁ ችላ ተብሎ የሚጣል አልነበረም፡፡በተለይ ለአባትሽ ብታስቢላቸው መልካም ነው ያለችው ዝም ብላ ከመሬት ተነሳታ አይደለም፡፡የእናቴ አባት ማለት አያቴ በእናቴ ላይ የነበረው ተስፋ እንዲህ ቀላልና ተራ የሚባ አይነት አልነበረም፡፡እሷ ላይ ብዙ ተስፋ ነበረው፡፡እናቷ በልጅነቷ ስለሞተች ከ10 አመቷ ጀምሮ ብቻውን ነው ያሳደጋት ፡፡ከዛን ጀምሮ ሚስት ላግባ አላለም….ከዛን ጀምሮ ለራሴ ምቾት ላስብ አላለም፡፡ጭንቀቱ እሷብቻ ነበረች፡፡ኢትዬጵዬ ይላታል፡፡አያቴ ሀገሩን ይወደል ፡፡ከሀገሩም እኩል ልጁን ይወዳል፡፡
አያቴ ኮረኔል ነው ፡፡በሀይለስላሴ የመጨረሻዎቹ ዘመን የውትድርናውን አለም ተቀላቅሎ በደርግ ሙሉ ከምስራቅ እስከሰሜን በተለያ አውደውጊያዎችና አገልግሎት ሰጥቶ ኢህአዲግ ሲገባ ጎደኞቹ ሲበተኑ አብሮ የተበተነ ግን ደግሞ እንደእድል ሆኖ ደህና ቤተሰብ ስለነበረው ወደትውልድ ከተማው ሲመለስ በመንደላቅ የሚያኖረው ንብረት ከቤተሰቦቹ በውርስ የጠበቀው ሰው ነው፡፡ እና አያቴ እሱ የጀመረውን ሀገርን ለእድሜ ልክ ማገልገል ልጁም በተለየ መንገድ ቢሆንም እንድትቀጥል ይፈልግ ነበር፡፡‹ጓደኞቼ ለዚህች ሀገር ህይወታቸውን ሰጥተዋል እኔ ደግሞ በአጋጣሚ በህይወት ቆይቼ ልጅ ወልጄ እንድስም ከተፈቀደልኝ ይህቺን ልጅ ለሀገር አገልጋይ እንድትሆን በስርዓት አሳድጌ ፤ በአግባቡ አስተምሬ እንሆ ኢትዬጵያዬ ልጄን እንደልጅሽ ተረከቢኝ ፡የደቀቀ ጎንሽን አሽታ ትጠግንልሽ ዘንድ፤የጎበጠ ወገብሽን ደግፋ ታቃናልሽ ዘንድ..እግርሽን ጣቶች መካከል የተጠቀጠቁትንና ያቆሰሉሽን እሾኮች ቀስ ብላ ህመምሽ እያማት በወረንጦ ለቅማ ታክምሽ ዘንድ ….የአይኖችሽን ዳር አይናሮች አፀዳድታ መታወርሽን በፈዋሽ ጠብታ እንድታድንሽ ዘንድ ….አዎ ህመምሽ ሚያማት፤ ጭንቀትሽ የሚጨንቃት ልጅ አድርጌ አሳድግን አስረክብሻለው፡፡ ብሎ ለዘመናት እየፎከረ አሳደጋት ፡፡ እንዳለው አድርጎ አስተማራት፡፡ዩኒቨርሲቲ ገባች በማእረግ ጨረሰጭ ፡በጥሩ ደሞዝ ጥሩ መስሪያ ቤት ተቀጠረች፡፡አያቴ ተኩራራ ..በራሱም በልጁም ስኬት ታበየ፡፡ድንገት ግን እናቴ ከጋብቻ ውጭ እኔን ፀነሰች፡፡አያቴ ደነገጠ፡፡ተወለድኩና ታየው፡፡ይበልጥ አንገቱን ደፋ፡፡በእኔ ሁኔታ ..ያንን ተከትሎ የእናቴ ስራዋን መልቀቅ ፤እቤት ኩርምት ብሎ መቀመጥ እና መላ ህይወቷን ለእኔ ለበሽተኛ ልጇ መስዋዕት ማድረግ አያቴን ከእርጅናውም ገፍቶ የሞት አፋፍ ላይ አደረሰው …አዎ ይሄ ደግሞ የእናቴን ጓደኛ ቢያሳስባት ያስመሰግናት ይሆናል እንጂ በክፋት አያስቀወቅሳትም…እናቴን ግን ከፋት
ለዚህም ነው -አይ ተስፋ ለሌለው ነገር እራስሽን መስዋዕት እንድታደርጊ ስለማልፈልግ ነው እንደዚህ የምልሽ..ደግሞ ለአባትሽም ብታስቢላቸው መልካም ነው::…ያለቻት
.እንዴት ተስፋ የሌለው ነገር ….?......እናቴ በገረሜታም በንዴትም ጓደኛዋ ላይ ተንዘረዘረች ፡፡
-ለምን ሁሉንም ነገር ዘርግፌ እንድናገር ታስገድጂኛለሽ..….?አሁን አራት አመት አልፎታል.. መናገሩ ይቅር ቢያንስ በእግሮቹ ቆሞ መረመድ ካልቻለ ምን ተስፋ ይኖረዋል፡፡ይሄ ከአዕምሮው ጋር ቀጥታ ግንኙነት ያለው ነው የሚመስለኝ››
-የልጅሽ አዕምሮውም አይሰራም እያልሽኝ ነው….?
-እንግዲህ እንደፈለገሽ ተርጉመሽ ተረጂው…ግን ለሚወዱሽ ሰዎች ስትይ ያልኩሽን ብታደርጊ እመርጣለው፡፡
-በቃ ውጪልኝ..ታያላችሁ ደግሞ ስንት ዓመትም ይፍጅ ስንት ዓመት ልጄ ቆሞ ይሄዳል፡፡ አንደበቱንም ከፍቶ ይናገራል….?አምላኬ በልጄ ላይ ታአምሩን እንደሚገልጽ አምናለው….የዘላለም አምላክ ፈጣሪ …ሁሉን አድራጊና ሁሉን መታሪ ኤልሻዳይ ለጊዜው ዝም ቢለኝም እስከመጨረሻው እንደማይረሳኝ እርግጠኛ ነኝ…የቅድስና እሳት የሚተፉ የማዳን እጆቹን የልጄ ሰውነት ላይ አንድ ቀን ያኖራል፣..አዎ ቀኑ ሲደርስ እንደዛ ያደርጋል››እናቴ በተለመደ መልኩ በፈጣሪዋ ላይ ያላትን እምነት በንዴት እየተንቀጠቀጠች ለጓደኛዋ አነበነበችላት
-አይ…ክርስቲያን ተስፋ አይቆርጥም ሲባል እኮ እንዲህ አይደለም….እንዲሁ የእናት አንጀት ሆኖብሽ ነው..››አላገጠችባት….እኔ ከዛ በላይ ታግሼ እናቴ እቅፍ ውስጥ ተዘፍዝፌ መቀመጥ አልቻልኩም..ወይንም አላውቅም እናቴ የምትተማመንበት ኃያሉ አምላክ እንደጠየቀችው ሚስጥራዊ እሷት የሚተፉትን የድህነት እጆቹን ሰውነቴ ላይ ጭኖብኝም ሊሆን ይችላል፡፡ብቻ የእናቴ ንግግር ተከትሎ በጉንጮቾ እየፈሰሰ ግንባሬ ላይ የሚንጠባጠበው እንባ ወደመሬት ከመውረድ ይልቅ ግንባሬ ላይ እያረፈ ወደ ህብረሰረሰሬ በመስረግ ውስጤን ሲያቃጥለኝ እና በዛው ቅጽበት የሆነ ነዛሪና የሚያንቀጠቅጥ አይነት ኃይል በሰውነቴ ሲራወጥ ታወቀኝ ..ከእናቴ እቅፍ ላይ ተወራጨው እና ተንሸራትቼ በአግሮቼ መሬት ረገጥኩ፡፡
እሷን ይዤ መሬት ረግጪ መቆም ሁሌ የማደርገው ስለሆነ ሁለቱም ትኩረት እልሰጡኝም…ግን ታአምራዊ በሆነ ፍጥነት የእናቴን ድጋፍ ለቅቄ የሩጫ ያህል እየተንደረደርኩ የሴትዬዋን የሚወናጨፍ እጅ ተንጠራርቼ ያዝኩና ወደውጭ እጎትታት ጀመር …..እናቴ እልልታዋን እያሰማች በጉልበቷ ተደፍታ መሬቱን ስትስም ጓደኛዋ ፃረሞት ፊት ለፊቱ እንደተጋረጠበት ሰው እጆን መንጭቃ ከእጆቼ በማስለቀቅ በሩጫ ከቤታችን አምልጣ በመውጣት ከውጭ የአጥር በራፍ ጋር ተላትማ ተዘረረች….

💫ይቀጥላል💫

ከወደዱት ከተመቾ Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሱ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3
#የመልስ_ጉዞ_ወደ_መነሻ
:
#ክፍል_አምስት
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

:
...አሁን እያወራዋችሁ ያለውት ተጨባጭ ስለሆነው እውነታ ነው፡፡ተጨባጭ እውነታ ማለት ምን ማለት ነው ካላችሁኝ በአምስቱ የስሜት ህዋሳቶች ተጠቅመን አዕምሮችን እንዲያስበው ወይም ልባችን እንዲሰማው ማድረግ የምንችለው ነገር ነው፡፡እርግጥ የሰው ልጅ አምስት የስሜት ህዋሳት ብቻ አይደለም ያሉት፡፡ብዙዎቻን የማንረዳውና ስድስተኛው የሆነውን የስሜት ህዋሳት ከተጨባጭ ዓለም ባሻገር ያለውን እወነታ የምን
…..አሁን ስለሌላው ችግሬ ልንገራችሁ..መናገር የቻልኩት ደግሞ በአስር አመቴ ነው፡፡ተገረማችሁ፡፡እውነቴን ነው ልክ እስከአራት አመት ስንፎቀቅ ኖሬ ድንገት ታምራዊ በሆነ መንገድ ብደግ ብዬ መሮጥ ጀመርኩ ፤በአስር አመቴም ድንገት በአንዴ ነው በሁለት ቋንቋ መናገር የቻልኩት፡፡አዎ ገብቶኛል አላመናችሁኝም አይደል፡፡እውነቱ ያነው፡፡
…የእግሬ ጉዳይ ተአምራዊ በሆነ አጋጣሚ እና ሁኔታ እልባት ካገኘ ብኃላ አንደበቴ ግን ባለበት ነበር የቀጠለው…፡፡ .አንዳንድ ትርጉም አልባ የሆኑ ድምፆችን ለምሳሌ ታታታ..ዳዳዳ የመሳሰሉትት ከአንደበቴ ለዛውም በጣም በምበሳጭበት ወቅት ይሰማ ይሆናል እንጂ የሚሰማኝ ስሜት የሚሰጥ ነገር ከእኔ አንደበት ማድመጥ ማይታሰብ ሆኖ ቀጠለ…..
በዚህ ሁኔታዬ የሰፈር ሰዎችም ሆኑ ዘመድ አዝማዶች የሆን በስህተት እንደተፈጠረ ሰው መሳይ ሸክም እንደሆነ ሰው ነበረ የሚያዩኝ፡፡ብዙዎቹ አዕምሮዬም ማሰብ የሚችል ሁሉ አይመስላቸወም ነበር፡፡‹‹ምን አለ ወዲያ ወስዶ በገላገላት ››ብሎ ለፈጣሪው መልሶ እንዲወስደኝ ስለት የሚሳሉ የእናቴ ወዳጆች ቀላል ቁጥር የላቸውም፡፡
ግን እነሱ ያልገባቸው የአዕምሮዬን የማሰብ ብቃት ስል መሆኑን ነው፡፡ከእግሮቼ እና ከአንደበቴ በልተጣጣመ መልኩ እንደውም ፍጽም ተቃራኒ በሆነ መንገድ አዕምሮዬ ክፉና ደጉን መለየት እና የሰላ እሳቤ ማሰብ የጀመረው ገና በጮርቃነቴ ነው ፡፡ይሄንን ግን ከእናቴ በስተቀር ማንም አይረዳልኝም ነበር፡፡እርግጥ አሁንም ድረስ ብዙዎቹ አያውቁም… ቢያውቁም ማመን አይፈልጉምን ፡፡
ከህፃንነቴ ጀምሮ እኔ የምጫወተው ዕቃ ዕቃ በመደርደር፤ወይም ከልጆች ጋር ሌባና ፖሊስ በመሯሯጥ ፤ወይንም ደግሞ ቡድን ለይቷ በሰፊ የሳር ሜዳ ላይ ከውሪ ህፃናት ጋር ተበትኖ በመሯሯጥ ኳስ በመጠለዝ አይደለም… ረጅም የተባለውን የልጅነት ጊዜዬን የቲቪ ስክሪን ላይ አፍጥጬ የተለያዩ አለማቀፍ የቲቪ ቻናሎችን በመከታተል ነው.....፡አረብኛ ቻናሎችን እንግሊዘኛ ቻናሎችን አማራኛ ቻናሎችን ወዘተ…
ከዛ የተረፈኝን ቀሪ ሙሉ ጊዜ ደግሞ በተመስጦ በማሰብ ነው የማሳልፈው፡፡ስለሆነ ነገር በጥልቀት እና በፍዘት ለሳዕታት በመተከዝ ማሰብ....ለዛውም ከተቀመጥኩበት ሳልንፎቀቅ እና አይኖቼን ከተከልኩበት ሳላንቀሳቅስ ..፡፡
የአማልክት ዝርያ ከሌለበት በስተቀር እስቲ አንድ የአምስት እና የስድስት አመት ልጅ በዚህ መልክ ሊያስባቸው የሚችላቸው ነገሮች ከየት ያመጣል…?፡፡ስለሆነ ነገር ለማሰብ እኮ ስለነገሩ ወይ በትምህርት ያገኙት ዕውቀት ካልሆነም በኑሮ ልምድ ያካበቱት የልምድ ክምችት ሊኖር የግድ ነው፡፡ከዛ ያንን መነሻ በማድረግ ስለነገሩ ይበልጥ ለመረዳት ወይንም ካወቅነው ጀርባ ያለን ድብቅ ወይም ሽሽግ ያልታወቀ እውቀትን ለመግለጽ ማሰብ ያለ ነው፡፡በዛ ላይ ለማሰብ እራሱ በመጠኑም ቢሆን የበሰለ አዕምሮ፤የዳበረ ስሜት ፤የበለፀገ እይታ ከሁሉም በላይ የፈካ ንቃተ-ህሊና አስፈላጊ ነው፡፡ሁሉም የሰው ልጅ ከማሰብ ችሎታ ጋር እንደሚፈጠር ባምንም ማሰብ እንደሚችሉ አውቀው በጊዜው ማሰብ የሚጀምሩ ሰዎች ግን ጥቂቶች እንደሆኑ አምናለው፡፡ ብዙዎቹ የማሰብን ፀጋ በተግባር ማጣጣም የሚጀምሩት በእርጅና ዕድሜ ውስጥ ከገቡ ቡኃላ ነው፡፡ወደኃላ በትዝታ እየተሳቡ እና በፀፀት እየተንገላቱ ፡፡ከዛም በባሰ ሁኔታ ከሚስጥራዊው አለም ይዞት የመጣውን ንጽህ አዕምሮ ሳይነካካው ይዞት የሚሞትም የሰው ልጅ ቁጥር ቀላል አይደለም፡፡በደመነፍስ ብቻ በመኖር፡፡
እኔ ታዲያ በተጋነነ ሁኔታ በጮርቃነት ዕድሜዬ እንዲያ ዓይነት ብስለት ከየት አመጣውት…? ይሄንን እናቴ ነች ምታውቀው፡፡ሌላውማ በዛ ሁኔተ ሲታዘበኝ እያሰብኩ እንደሆነ ሳይሆን የሚረዱት በአዕምሮ ዝግመት በሽታ ተጠቅቼ እየነሆለልኩ እንደሆነ ነው፡፡ለነገሩ ማን ነበር ‹በጂኒዬስነትና በእብደት መካከል ያለችው መስመር በጣም ቀጭን ነች ያለው ››….በዚህ እሳቤ እንደእብድ እኔን ማሰባቸው ብዙም አልተሳሳቱም፡፡

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3👏1
#የመልስ_ጉዞ_ወደ_መነሻ
:
#ክፍል_ስድስት
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
..… እንደነርኮችሁ የመራመዴ ጉዳይ ተአምራዊ በሆነ መንገድ እልባት ካገኘ ቡኃላ እናቴ ለአንደበቴ መከፈት መጓጓት ጀመረች፡፡ያው እናት አይደለች ፡፡በተለይ ስድስት አመት ከሞላኝ ቡኃላ እኩዬቼ ሁሉ ወደትምህርት ቤት ሲጓዙ እኔ አንደበቴ መላቀቅ ባለመቻሉ ምክንያት እቤት በመቅረቴ ውስጧ ተጎዳና እንደአዲስ እኔን ለማዳን የምታደርገውን እንቅስቃሴ ጀመረች ፡፡በዚህ እንቅስቃሴዎ ወቅት ስታልፍም ሆነ ስታገድም የሚያገኞት ሰዎች ሁሉ የሆነ ነገር ሳይሏት ዝም ብለው አያልፎትም፡፡
መቼስ ሀበሻ ባህል ውስጥ አንዱ አስቸጋሪው ነገር የሆነ ሰው ችግር ላይ በወደቀ ቁጥር ምክር ሰጪ ሰው መብዛቱ የታወቀ ነው፡፡ለምን ጠበል አትወስጂውም……?አዋቂ ቤት ይሻልሻል……?እዚህ ከተማ ላይ አዲስ ሀኪም መጥቷል አሉ….…? ውጌሻ ጋር አይሻልሽም….የማይባል ነገር የለም፡፡ታዲያ ይሄ ችግር ውስጥ ላለችና ግራ ለገባት እናቴ በወቅቱ ምን ያህል ግራ አጋቢና አስጨናቂ እንደሚሆንባት መገመት አይከብድም፡፡
እናቴ አንደወትሮዋ እኔን ለማዳን ስትንከራተት ውላ ስትመለስ አባቷ ይናገራታል፡፡
-ልጄ በቃ ለአምላክ ተይው…እሱ እንዳደረገ ያድርገው
-እንዴት እንዳደረገ ያድርገው ስትል…?...ትጠይቃለች
-በቃ አንዳንዴ ከአምላክ ጋር እልክ መጋባት አያስፈልግም…አሱን አድናለው ብለሽ ከእዚህ እዛ ስትካለቢ አንቺም ከሰውነት ጓዳና ወጣሽ…እራስሺን እስኪ እይ… የአርባ አመት አሮጊት መስለሻል እኮ…ገና በሀያ ሶስት አመትሽ ፊትሽን ማድያት እየበላው ነው፡፡በዚህ ከቀጠልሽ የከፋ በሽታ ላይ መውደቅሽ አይቀርም፡፡
-እና ምን አድርጊ ነው የምትለኝ፡፡…?
በቃ እሱን አድናለው ብለሽ ከወዲህ ወዲያ መንከራተቱን አቁሚ.. እግዜያብሄር እግሩን ተርትሮልሻል …በቃ በዛ ተመስገን ብለሽ ሌላውን ተይው…ይሄው ለዓመታት ተንከረተሽ፡፡ ..ህክምናውንም ጠበሉንም ሞክረሻል፡፡ይሄ ነው ችግሩ ብሎ ሊነግርሽ የቻለ የህክምና ጠቢብ የለም፡፡ይሄ ማለት ደግሞ የልጅሽ ችግር ሚስጥር በአምላክ እጅ ብቻ እንደሆነ ነው የሚገባኝ፡፡ በእሱ እጅ ከሆነ ደግሞ ታአምሩን የሚያደርግበት የራሱ ቀንና ጊዜ አለው፡፡እሱን በትዕግስት መጠበቅ ነው፡፡ስለሆነም መንከራተቱን አቁሚ፡፡እዚሁ እንከባከበዋለን፡፡ምንም ነገር እንዳይጎልበት ማድረግ እንችላለን፡፡የሚጠብቁት ተጨማሪ ሰራተኞችም ልንቀጥርለት እንችላለን፡፡አንቺ ግን ከዚህ በላይ እራስሽን አትጣይ፡፡ ……
-አባዬ እናቱ እኮ ነኝ፡፡እንዴት ይሄ የእግዜር ስራና ፍቃድ ነው ብዬ እጆቼን አጣጥፌ ተስፋ ቆርጬ ልቀመጥ እችላለው…?፡፡አንተ እኔ እንደዛ ብሆንብህ የሆነችውን ትሁን ብለህ ተስፋ ቆርጠህብኝ ትተወኝ ነበር…?፡፡…….የትዝብት ጥያቄ ጠየቀቺው፡፡
-አይ…ስለልጅ ልጄ እኮ ነው እያወራን ያለነው… ለአንቺ ብቻ ሳይሆን ለእኔም ልጄ ነው፡፡ጨካኘ ሆኜ አይደለም፡፡ግን እሱን ለማደን በሚል ያልተረጋገጠ ተስፋ አንቺን እንዳላጣ ስለፈራው ነው፡፡ሰለጨነቀኝ ነው፡፡
-በቃ አባዬ በቃ …. መቼም በልጄ ተስፋ አልቆርጥም፡፡መቼም እግዜር እንዳደረገ ያድርገው ብዬ ልቤን አረጋግቼ እድሜ ልኩን ከሰው ተገልሎ በተዘጋ ቤት ውስጥ እንዲኖር በመፍረድ እኔ ለመሽቀርቀርና እራሴን ለማሽሞንሞን አልሞክርም…..መቼም፡፡……ብላ ከአባቷ በንዴት እና በለቅሶ ተለይታ እኔን ወደመኝታ ቤት ይዛ ገብታ ግንባሬ ላይ ተደፍታ በእንባ እየታጠበች ከፈጣሪዋ ጋር ለሳዕታት በምሬት ካወራች..(እናንተ ከፀለየች )ብላችሁ ማንበብ ትችላላችሁ አቅፋኝ ትተኛለች፡፡
ማለዳ ሊነጋጋ ሲል ጥርት ያለ ህልም ታያለች፡፡ተመሳሳይ አይነት ህልም እኔም አይቻለው፡፡ልዩነቱ እሷ ያየችውን ህልም ለአባቷ መናገር ስትችል..እኔ ደግሞ ምናገርበት አንደበት ስላልነበረኝ ለእሷ እንኳን መናገር አልቻኩም፡፡
-ህልሙ እንዲህ ነው
ጠይም የተለጠለጠ ኑግ የሚመስል የሰውነት ቀለም ያላቸወ ፊታቸው በአደገ እና በተንዠረገገ ነጭ ፀጉር የተሸፈነ ሽማግሌ መኝታ ክፍላችን ሰተት ብለው ይገባሉ፡፡እናቴ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጣ እኔን ጉልበቷ ላይ ታቅፋ በተመስጦ ላይ ሳለች ሰውዬው ወደእኛ ቀርበው ወለሉ ላይ በርከክ ይሉና ጭንቅላቴን እየዳበሱ
‹‹ ..ልጅሽ ታላቅ ሰው ይሆናል፡፡አንድ ቀን ዓለም ስለእሱ በመደመም ያወራል፡፡ምድራዊውን አለም ከመንፈሳዊው አለም ጋር ድልድይ ሆኖ ያስተሳስራል…ስለዚህ አንቺ መጨነቅሽን አቁሚ .. እሱ በፈለገ ቀን እራሱን ማዳን ይችላል፡፡ ከራሱም ተርፎ ሌላውን ያድናል፡፡ግን ሲፈልግ…ቀኑ ሲደርስ ብቻ ነው እንደዛ የሚያደርገው፡፡
-አባት ስለእኔ ልጅ ነው የሚያወሩት..?በጥርጣሬ እና ያሉትን ባለማመን ትጠይቃለች፡፡
-አዎ ልጄ ..እኔ የአማላክ መልዕክተኛ ነኝ፡፡ አምላክ እንደገለፀልኝ ከሆነ የልጅሽ እውቀት ጥልቅና ከዛኛው አለም ይዞት የመጣው ነው፡፡
-ከዛኛው አለም ሲሉ…?፡፡
ዳግመኛ ስለመወለድ የምታውቂው ነገር አለ ልጄ.?.
-እኔ እንጃ ብቻ ከዚህ በፊት የሰማው መሰለኝ፡፡አዎ ክርስቲያን አይደለው..ሰው ከውሀና ከመንፈስ ዳግመኘ ካልተወለደ በስተቀር ወደመንግስቱ መግባት እንደማይችል አምላክ ተናግሯል፡፡
-ትክክል እኔ ግን እያልኩ ያለውት ልጅሽች ወደ እዚህች ምድር ሲመጣ ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡ ከሁለት ሺ አመታት በፊት ነፍሱ እዚህች ምድር ላይ ነበረች…የበለፀገ ህይወት እና በእውቀት የተሞላ ስብዕና ነበረው..እና ያንን እውቀት ነፍሱ ይዛው የመጣች ይመስለኛል፡፡
-እና እኔ ምን ላድርግ …?
-ምንም ፤እራሱ ፈልጎ የሆነ ነገር ማድረግ እስኪችል ድረስ አትጫኚው..አንቺም አትባክኚ፡፡ ብቻ በእሱ ላይ ሁሌም እምነት ይኑርሽ..ወስጡ የተቀበረውን እውነትና እውቀት ብቻ እንዲገለፅለት ሁሌ ከጎኑ ሁኚ…ከጎኑ መሆንሽ ብቻ ለእሱ በቂው ነው..ሌላውን በጊዜው እራሱ ያደርገዋል፡፡
-ሽበታሙ መልዕክት አድራሽ ሽማግሊ ከክፍላችን ሳይወጣ ነበር የሰራተኛችን የመኝታ ቤታችንን በራፍ መቆርቆር ሁለታችንንም ከእንቅልፋችን የቀሰቀሰን
-እናቴ ህልሙን ልትረሳ ሰውዬውንም ልትዘነጋ አልቻለችም፡፡ሰራ አልቻለችም..ሰውዬውን ልትዘናጋ.
ዘወትር እንደምታደርገው ማታ አካባቢ ቤተክርስቲያን ሄድን፡፡የተለመደውን የማታ ትምህርት ተከታትላ..ያው እንደወትሮዋ ከአምላኮ ጋር አንሾካሽካ ፤ስትጨርስ ስለህልሞም እያሰበች የመልስ ጉዞ ለማድረግ የቤተክርሲቲያን አጥር ግቢ ወጥተን ብዙም ሳንርቅ እኛ ሁለታችንም በህልማችን ያየናቸው ሽማጊሌ በትክክል እሳቸው ድንገት ከፊታችን ተደንቅረው መንገዳችንን ገቱት.እኔ ብዙም ባይደንቀኝም እናቴ ግን በድንዛዜ ሀውልት መስላ ነበር ባለችበት የቆመችው
-ሰውዬው ለእናቴ ድንጋጤ ብዙም ትኩረት ሳይሰጡ ጎንበስ ብለው እጃቸውን ጭንቅላቴ ላይ አሳርፈው በመዳበስ እይታቸውን ወደእናቴ አድርገው ‹‹ጌታ ችግርሽን ይፍታልሽ…እግዜያብሄር ለቅሶሽን ሰምቶል ››በማለት የብስራት ቃላቸውን አሰሟት
-ተአምር ነው፡፡እርሷ መላአክ ኖት…?
-አይ አይደለውም ሰው ነኝ፡፡ተራ ሰው ለሶስት ቀን በተከታታይ በህልሜ ሳያችሁ ነበር፡፡ህልሜን አምኜ እዚህ ስመጣ ደግሞ በአካል አገኘዋችሁ፡፡››
-እኔም አይቼዎታለው››
-በይ እንግዲህ የምኞትሽ ይሙላልሽ ?
-በህልሞት ምንም እንዲነግሩኝ አልተነገሮትም.››
-አይ ሁሉንም ለእሷ ነግሬያታለው..አንተ ብቻ አግኛትና ልጇን ደባብስላት ነው የተባልኩት፡፡……..ብለው አልፈውን መንገዳቸውን ሲቀጥሉ…እናቴ ከድንዛዜዋ ባና -እሺ እግዜር ይከተሎት..አለቻቸው
-አንቺንም ልጄ....ከእነልጅሽ እግዜያብሄር ይጠብቅሽ ፡፡ብለው ከእይታችን ተሰወሩብን
ከዛ ቡኃላ እናቴ ፍፁም ተረጋጋች
👍4
በእኔ ላይ ያላትም እምነትና ተስፋ እንደአዲስ ደርጅቶ አበበ፡፡በዛም መሰረት እንደማንኛውም ልጅ በ7 ዓመቴ አንደኛ ክፍል አስገባቺኝ ፡፡

💫ይቀጥላል💫

አረ Like እየቆጠባቹ ነው 👍👍 Like እያደረጋቹ እንጂ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
#የመልስ_ጉዞ_ወደ_መነሻ
:
#ክፍል_ሰባት
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
ትምህርት ቤት ገባው፡፡መናገር ባልችልም የምማረው ከተናጋሪዎች ጋር ነበር፡፡አርግጥ ተማሪዎቹም ሆነ አስተማሪዎቹ ብዙም አይጥሙኝም፡፡ትምህርቱም እንደዛው ፡፡ግን ተማርልኝ ያለቺኝ እናቴ ስለሆነችና እሷ ያለቺኝን ነገር ሁሉ ተመቸኝም አልተመቸኝም …አስደሰተኝም ፤አስከፋኝም ማድረግ ስላለብኝ ነው ያደረኩት፡፡
አንደኛ ክፍል አንደኛ ሴሚስተር በከፍሉ ካሉት 56 ተማሪዎች 55ተኛ ደረጃ ወጣው ፡፡የበለጥኩት አንድ ልጅ በመጨረሻዎቹ የፈተና ቀኖች ትምህርት ቤት ተገኝቶ ዋናውን ፈተና መውሰድ ስላልቻለ እና ካርዱ ላይ የተቀመጠለት ውጤት ቴስት ላይ ያገኛቸው ውጤቶች ብቻ ነበሩ፡፡
እኔ ባመጣውት ውጤት ማንም አልተደነቀም ምክንያቱም ማሰብ እንደምችል እራሱ የሚያምን ሰው ጥቂት ነው፡፡ማሰብ ማይችል ሰው እንዴት መማር ይችላል ብለው ይገምታሉ…?፡፡ ካርዴን ይዤ መጥቼ ለእናቴ ስሰጣት እቤቱ ሙሉ ወዳጅ ዘመድ በተሰበሰበበት ነበር፡፡ልክ ድንበር ሊወር የመጣን የጠላት ወታደር ፊት ለፊት በጀግንነት ተፋልሞ በማሸነፍ የድል ብስራት ለወገኖቹ እንደሚያስር ወታደር ደረቴን በኩራት ገልብጬ…
-አይ ዝም ብለሽ እኮ ነው የምትለፊው…..እቤት ከነበሩት መካከል አንዱ ዘመድ የተናገረው ነበር..
-እንዴት ዝም ብዬ…?
-ትምህርት እኮ ለእሱ ይከብደዋል፡፡እንዲሁ ከልጆች ተቀላቅሎ ይዋል ብለሽ እንደሆነ ይገባናል፡፡ግን ማሰብ ያለብሽ ወደሁለተኛ ክፍል ለመዘዋወር ስንት አመት ይፈጅበታል የሚለውን ነው……?ሶስት……?አራት….…?
.
-ለእኔ ስሜት ሳይጨነቁ እንደአፌ አእምሮዬም ዝግና ዱልዱም መሆኑን እርግጠኛ ሆነው እናቴን የሚያሳቅቁበት መርዝ ንግግር ሰነዘሩ..
እናቴ ከተቀመጥኩበት ወደራሷ ስባኝ ጭኖቾ ላይ በማጋደም ጭንቅላቴን እየዳበሰች…
-ልጄ በአመቱ መጨረሻ ወደ ሁለተኛ ክፍል በበቂ ውጤት አልፎ ካልገባ እኔ ላይ ሳቁብኝ፡፡…አለቻቸው እሷም ልክ እንደእኔው ጀግና ልጅ እንዳለት እርግጠኛ በመሆን ደረቷን ነፍታ..
-አረ ተይ የማይሆነውን ….ብለው ወዲያውኑ ሳቃቸውን የለቀቁት በርከት ይሉ ነበር….እኔ ግን የእናቴ ንግግር ትንሿን አዕምሮዬን ሰንጥቆ ነበር የገባው፡፡‹በዓመቱ መጨረሻ ልጄ ወደ ሁለተኛ ክፍል ካላለፈ ሳቁብኝ›…ፃድቋ እናቴ ላይማ ማንም አይስቅባትም…..ወሰንኩ፡፡
-ማታ ብቻችንን ሆነን ደረቷ ላይ ተኝቼ ማስበው ወደ ሁለተኛ ክፍል ስለማለፍ ነበር፡፡
-ምን ማድረግ አለብኝ…?፡፡በአንደኛ ሲሚስተር እንዴት እንደተማርኩና …?እንዴት እንደተፈተንኩ…? አሰብኩ.. አስተማሪዎች ሲያስተምሩ አንድም ቀን አዳምጬያቸው አላውቅም…አንዳንድ ቀን በመስኮት አሻግሬ ሜዳ የሚጫወቱትን ልጆች ወይም ዛፍ ላይ አርፋ የምትዘምረዋ ወፍ ወይም በሰማይ ላይ የሚጓዘውን ደመና ስመለከት ነው ክፍለ ጊዜው የሚያልቀው፡፡አንዳንዴ ደግሞ ወረቀት ቀድና በምራቄ አለስልሼ ጆሮዬ ውስጥ ጠቀጥቃለው..
---አንድ ቀን ይሄንን ሳደርግ እጅ ከፍንጅ የያዘኝ አንድ መምህር..አንደበትህን እንደዘጋው ጆሮህንም እንዲደፍንልህ ትፈልጋለህ…ሲል ጠየቀኝ በመገረምና በንዴት አፍጥጦብኝ
ግንባሬን በመወዝወዝ‹‹አዎ…›› የሚል ምልክት አሳየውት
አማተበና‹‹አንተንስ ትልቁ አጋንንት ነው የተጠጋህ ››ብሎኝ ወደማስተማሩ ተመለሰ…..ከዛን ቀን ቡኃላ ጭራሽ የዛ ክፍል ተማሪ እንዳልሆንኩ በመቁጠር ረሳኝ … እኔም ተመቸኝ..፡፡
ስለዚህ አሁን በዓመቱ መጨረሻ እኚ ወሬኞች እናቴ ላይ እንዳይስቁባት..አስተማሪዎች የሚሉትን ትንሽ ትንሽም ቢሆን ማዳመጥ መጀመር አለብኝ ብዬ ወሰንኩ፡፡
የትምህርት ዘመኑ ተጠናቆ ..ሰኔ ሰላሳ መጥቶ የወላጆች በዓል ላይ ያልታሰበ ነገር ተከሰተ….ልዩ ተሸላሚ ሆኜ መድረክ ላይ ተጠራው.. ሰው ሁሉ የፀባይ ሽልማት መስሎት ነበር..ያው ድዳ በመሆኔ ተናግሬ መበጥበጥ ስለማልችል በተጨማሪም በፀባዬ ጠማማነትም የተነሳ ከልጆች ጋርም እንደማልገጥም ብዙዎች ስለሚያውቁ የፀባይ ሽልማትማ ይገባዋል… ብለው ነበር ያሰቡት፡፡
-የትምህርት ቤቱ ዳሪክተር ግን እኔን ስራቸው አቁመው ጭንቅላቴን ልክ እንደ አባት እየዳበሱ በአስገምጋሚ ሻካራ ድምፃቸው የትምህርት ቤቱን ግቢ ለሞሉት ተማሪዎቻቸውና ወላጆቻቸው መናገር ጀመሩ…
***
በ25 ዓመት የማስተማር ልምዴ እንዲህ አይነት ተአምር ገጥሞኝ አያውቅም፡፡ማመን አቅቶን ውጤቶቹን ሁሉ ደግመን ፈትሸን ነበር የሚገርመው ምንም እንከን አልተገኘባቸውም ፡፡በአንደኛ ሴሚስተር ከክፍሉ የመጨረሻውን ደረጃ ነበር የያዘው…
ኹ ..ሁሁሁ ብሎ ታደሚው ሁሉ አውካካ..
በዚህኛው ሴሚስተር ደግሞ አንደኛ ….ከሰባት ትምህርት ስድስቱን መቶ.... አንዱን ዘጠና ስምንት ነው ያመጣው፡፡አማካኝ ደረጃው 23ተኛ ደረጃ ፡፡እንዲህ አይነት ለውጥ በማምጣቱ ትምህርት ቤታችን እንዶኮራበት ወላጆቹም ልትኮሩበት ይገባችሆል..በቀጣይ በዚሁ እንዲቀጥልም አስፋላጊውን ድጋፍ አድርጉለት ..በማለት ከአቅሜ በላይ የሚከብድ መዝገበ ቃላት በሽልማት መልክ አሸከሙኝ››
መድረኩን ለቅቄ እየወረድኩ እናቴን አየዋት… ከአምስት ወራት በፊት ሳቁብኝ ብላቸው ወደነበሩ ወዳጆቾ ዞራ ቅዱስ የእርካታ ሳቅ እየሳቀችባቸው ነበር….እኔም በፈገግታ አገዝኳት።

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍7
<<ነ>>

ሀገርን የሚያክል ህላዊ እያለነ፤
በዘርና ብሄር በጎጥ በሀይማኖት፤
ተሸነጋገልነ፤
ተፈነጋገልነ፤
የኔ የሱ የሷ የኛ ኬኛ እያልነ፤
ይሄው ይሄኛውን ሳብነ፤
ያኛውን ገፋነ፤
አለቅጥ ዘቀጥነ፤
አለቅጥ ጠበብነ፤
ምነ ! ምነ! ምነ !
እንዲህ የወረድነ፤
እንዲህ የጠበብነ፤
ቀን በየሄድንበት፤
ሌት በተኛንበት በየትም አቅጣጫ፤
እንደያለንበት፤
አለቅጥ ጠበነ፤
አለቅጥ አንሰነ፤
እንጨነቅበት እንሰራው ጠፋነ፤
እንሆነው አጣነ፤
በዚ ሆነ በዛ ራስ ወዳድ ሆነ፤
ራስ አበዛነ ባገኘነው ሁሉ አንድነት ትተነ፤
ስንወጣ ስንገባ ጎጥ እየነዛነ፤
ዘር እየመዘዝነ፤ህዝብ አሰቃየነ
ሀገር አሸበርነ፤
ምነ! ምነ! ምነ!
እንደዚ ታወርነ፤ለማጥላት አንዱነ
ጉድጓድ እየማስነ፤
አንዶንዱን ለመነጥነፍ ነፍጥ እየተኮስነ፤
ታሪክ በርዘን፤
የማያግባባነ ታሪክ እየፃፍነ፤
የሚለያየነ፤ስልት እየደፈነ፤
እጅጉን አነሰነ፤ነጥብን አከልነ፤
ከልፍነት ወጣነ፤
ምነ !ምነ ምነ !
እንደዚ የጠበብነ፤እንደዚ ያነስነ፤
ሌላው ስለአንድነት፤አለም ስለህብረት፤
እየተጨነቀ የኛ ግን አንድነት እያደር ሟሸሸ
እያደር አለቀ ምነ ! ምነ ! ምነው ! አረ ምነ!
እንዲህ የጠብነ ይሻልን ትተነ፤
አንዷዱን መክሰሻ ቅጥያ፤
እንደጆሮ ሰርክ እየለጠፍነ፤
ዱላ ለመማዘዝ ጥይት ለመታኮስ፤
ጥላቻ ሌት ተቀነን እያሰራጨነ፤
ፍቅር እየገፋነ፤ ቂም እየገዛነ፤
መተሳሰብ ይሉት ባፍጢሙ ደፍተነ፤
ትብብር ሲያሻነ፤ንጥጥል መርጠነ፤
መደማመጥና በሀሳብ መላቅን
ሺ ክንድ እርቀነ፤
በነጋ በጠባ አጀንዳ ፈጠርነ
ቂምን አባዛነ፤ ተንኮልን ነደፍነ፤
የተረሳን ቁስል ብሶት ቀሰቀስነ፤
ምነ ! ምነ ! ምነ !
እንደዚ ጠበብነ፤
ምነ ! ምነ ! ምነ !
ፍቅር እንደሰማይ እንዲህ የራቀነ
ምነ ! ምነ ! ምነ !
እንደዚህ ያነስነ፤
ካገራችን ይልቅ የጎሳችን ጉዳይ ሰርክ አስጨነቀነ፤
ባለመደማመጥ ሽኩቻ ታመስነ፤
ተንኮል በመጎንገን በሴራ ታመምነ፤
ጠበብነ፤
ጠበብነ፥
ይሄው ከልክ አልፎ፤
በየኛና ኬኛ ህዝብ አወዛገብነ
እናት አስጨነቅነ፤ አገር አሸበርነ፤
ምነ! ምነ!ምነ! ምነው !አረ ምነ!
ማን ረገመነ ?
የሀሳብ ቋንጃችን ተበተበ በነ፤
መላወሻችንን ማን አሰረብነ፤
ትላንትን ዘክሮ፤ ዛሬን ተተርሶ፤
ነገንም አስታውሶ፤
ከታሪክ ፈልፍሎ መፍትሄ የሚያመጣ
አንድ ሰው ያጣነ፤
እውነት ግን እናተ ማን እረገመነ ?
ምነ! አረ ምነ!
ያገር ውላችንን ማን ቋጠረብነ ?
እንዲህ በአጭር ጊዜ፤
ተስፋችን በጠዋት ጉም ሸፈነበነ፤
አምና ይሄን ግዜ ከመቶ ሚሊዮን
አንድ ሰዉ ስጠነ ብለን ተጨንቀነ፤
ከዚህ የጭንቅ ውሀ የሚያሻግረነ፤
ከፍቅር ደሴት ዘንድ አቅፎ የሚያደርሰነ፤
የኛ ዘመን ሙሴ አገኘን ብለነ፤
በየአደባባዩ እንዳልተሰለፍነ፤
አኛ እንሙት ብለነ፤
ቦንብን ያህል ነገር ካየር ላይ ቀልበነ፤
እንዲያ እንዳልቆሰልነ፤
ወይም እንዳልሞትነ፤
እናዳልተሰዋነ፤ አመት ሳይሞላነ፤
ከዚያኔው ሰቀቀን የባሰ፤
የሚመስል የጨነቀ ነገር ምነ ገጠመነ፤
ጎራ ለይተነ አንደኛው ካንደኛው፤
እየተቧደነ አንገት ለመቀንጠስ ምነ ተፋለግነ፤
ወደ ነበርንበት ወደዛ ክፉ ቀን መመለስን ሻትነ፤
ምነ ! ምነ ! ምነ !
ፍትህን ብለነ ለውጥ ይምጣ ብለነ፤
በጎንደር በአንቦ በአገር ዙርያ ገባ፤
ደሙ ደማችን ነው እዳልተባባልነ፤
በጋራ ሁነነ እየተባበርነ፤
እየተሳሰብነ የጨለማውን ቀን እናዳልቸሻገርነ፤
ባይዞህ አይዞህ እታ ክፉውን፤
አቀበት እንዲያ እንዳልወጣነ፤
የለውጥ አየር ሲነፍስ ምኑ ዞረብነ፤
ምን ሰይጣን ገባነ፤
ባቢሎን ሆነን የኛ ኬኛ የሚል ቋንቋ አደባለቅነ፤
አረ እንደማመጥ አረ እንነጋገር፤
ምነ ! ምነ ! ምነ ! ምነው? አረ ምነ !
የትላት ጥንቡሳስ ምነ ቢበቃነ፤
ለትላንት አዙሪት ባትመልሱነ፤
ምነ ! ምነ ! ምነ !
አረ በፊደሏ አረ በ ነ ! በ ነ !
ጠዋት ማታ ስጋት እንደጨው ሟሟነ፤
መሞት መፈናቀል ሆነ እጣችነ፤
ምነ ! ምነ ! ምነ !
ባታስጨንቁነ፤ አንድ አመት ሳይሞላ
እንዳምና ካቻምናው አታሸብሩነ፤
አረ በፊደሏ አረ በ ነ! በ ነ!
በብሄር መናቆር ስለሰለቸነ፤
ስላሳቀቀነ አታለያዩነ፤
አታነጣጥሉነ፤ አታበላልጡነ፤
ይልቅ በኩልነት ወደ ፊት ምሩነ፤
ያንድ ኢትዮጵያ ልጆች እኛ ሁላችንም፤
ከዘራችን በፊት፤
ሰው ነነ ! ሰው ነነ !!

💚 💛 ❤️
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_ስምንት
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ከዛ ቡኃላ የትምህርት ቤቱ አስደናቂ ኮከብ ተማሪ ሆኜ ቀጠልኩ ፡፡እስከሶስተኛ ክፍል እስካጠናቅቅ ድረስ አንደበቴ እንደተዘጋ ነበር፡፡አስር አመት ከሆነኝ ቡኃላ አንድ ለሊት እኔና እናቴ የሰላም እንቅልፍ ተኝተን እያለ…ባልተለመደ ሰዓትና ሁኔታ የቤታችን መንጓጓት ሁለታችንንም እኩል ከእንቅልፍችን ቀሰቀሰን…. ሁለታችንም እኩል ዙሪያችንን ስንቃይ እቤቱ በድቅድቅ ጨለማ እንደተዋጠ ስለነበር ምንም ሊታየን አልቻለም … መብራቱን ለማብራት እኔም እናቴም እልደፈርንም….. …እናቴ ከክንዷ ላይ እኔን በማውረድ ከእቅፎ አውጥታኝ በዝግታ በመነስታ እና ቁጭ በማለት ምን እንደተፈጠረ ለማረጋጋጥ ጆሮዋን አቀናች..እኔም እሷን ተከትዬ ለመነሳት ስሞክር በእጇ ደፍቃ ባለውበት አስቀረቺኝና ወደጆሮዬ ተጠግታ በሹክሹክታ‹‹..አርፈህ ትንፋሽህን ውጠህ ተኛ..››በማለት አስጠነቀቀቺኝ …
ወዲያው የመኝታ ቤቱ በራፍ ሲበረገድና ባትሪ ግንባራችን ላይ ሲበራ እናቴ ‹ዋይ› የሚል ድምጽ አሰምታ ‹ልጄን ›በማለት እኔ ላይ ድፍት አለች
…ሁሉም ቅፅበታዊ ነበር…ውር ውር የሚል የባትሪ ብርሀን ግድግዳው ላይ ወዲህ ወዲያ ሲራወጥ እና የእግር ኮቴ ሲዘዋወር ይሰማኛል…
‹‹በል ፈትሽ ..ኮመዲኖውን ክፈት››ድምጽ ተሰማ
‹‹እንቀሳቀሳለው ብለሽ አንቺን ሳይሆን ልጅሽን ነው ፀጥ የምናደርግልሽ..››ሌላው እናቴን አስፈራራ…..
እናቴ የራሷን ትንፋሽ ወደውስጧ ማፈኗ ሳያንሳት እኔንም እላዬ ላይ እንደተደፋች በእጆቾም አንደበቴን ከደነችው፡፡
‹‹-አዎ ሁሉንም በሻንጣ ክተት..አዎ ወርቅም አገኘህ…ጥሩ ልብሶቹንም እንዳትተው››ይላል
ሶስት መሆናቸው በድምጻቸው ልዩነት ገምቼያለው፡፡ያው መዘረፋችን ቢያሳዝነኝም ዋናው እናቴን አለመጉዳታቸው ነው ብዬ በመጽናናት ስራቸውን እስኪጨርሱ እናቴ እንዳፈነቺኝ ታፍኚ በተኛውበት ተረጋግቼ የሚያደርጉትን ማየት ባልችልም የሚናገሩትን በትዕግስት እየሰማው ሳለ
በቃ እንሂድ ››በማለት አንዱ የመጡበትን ማጠናቀቃቸውን አበሰረን….››እፎይ ምንልበት ጊዜ ደረሰ.. ስል ተደሰትኩ
‹‹በል እናትዬውን እሰራት..አፎንም አሽገው››የሚል ደባሪ ድምጽ ወደጆሮዬ ገባ
‹‹ለምን አስፈለገ.…?.››ሌላው ጠየቀ
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ ..ከዚህ ሳንወጣ ጩኸቷን ብትለቀውስ…?›› ስጋቱን ተናገረ
‹‹እናንተ ብቻ የያዛችሁትን ይዛችሁ በሰላም ውጡልኝ …በልጄ ምላለው ምንም አልጮህም››እናቴ ተማፀነቻቸው
አንደኛው‹‹ዝም በይ..›› ብሏት በምኑ እንደሆነ አላውቅም ከላይ ወገቧን ሲነርታት የህመሙ ስሜት ከስር ያለውትን እኔን ሳይቀር ተሰማኝ …
‹‹ና በል አንሳትና ከእዚህ የአልጋ እግር ጋር ጠፍንገህ እሰራት …ልጇንም እንደዛው….››ሲለውና ሌላው ትዕዛዙን ለማክበር እናቴን መንጭቆ ከላዬ ላይ ሲያነሳት ..የሆነ የማላውቀው ኃይል በሰውነቴ ሲሰራጭ ታወቀኝ
…እናቴ ‹‹ልጄን … ልጄን እንዳትነኩብኝ ››..እያለች ስትወራጭ…የድምፆ ቅጭልጭልታ ጆሮዬን እየነዘረ ወደጭንቅላቴ ሲሰርግ እና የሆነ የማላቀውቀው መንፈስ ሲቆጣጠረኝ አንድ ሆነ…..
ወደእኔ ከመምጣታቸው በፊት ተሸከራከርኩና በተቃራኒው በኩል ከአልጋው ተንከባልዬ ወረድኩ …… አዛዥ ቢጤው‹‹ልጁን ያዘው.. ልጁን ያዘው›› ሲል ይሰማኛል፡፡ አልጋውን ዞሮ ወደእኔ ከመምጣቱ በፊት ለእኔም ግልፅ ባልሆነልኝ የደመነፈስ ውሳኔ እና የእኔ ባልሆነ ፍጥነት የቁም ሳጥኑን መሳቢያ ስቤ ሽጉጥ አወጣውና ወዲያው መብራቱን በማብራት በኮማዲኖ በራፍ መላ አካሌን በመከለል ጭንቅላቴን ብቻ በከፊል ብቅ አድርጌ ሁኔታውን ቃኘው ….፡፡አዎ እንደገመትኩት ሶስት ናቸው፡፡ሁሉም ፊታቸው ላይ ጭንብል አጥልቀዋል፡፡ግን የጠበቅኮቸውን ያህል አስፈሪና ወጠምሻ አይነት አይደሉም…አንዱ የብረት ዱላ ሁለቱ ጩቤ ይዘዋል፡፡አንዱ በራፉ ጋ ቆሞ በቀኝ እጁ የያዘውን ባትሪ እኔ ወዳለውበት ቀስሯል፡፡ማብራቱን ካበራው ቡኃላ እንኳን አላጠፋውም..ሌላ እናቴን እያሰራት ነው..ሶስተኛው ሊይዘኝ ወደእኔ እየተንደረደርረ ነበር ..ሊያንቀኝ ሁለት ሜትር ያህል ብቻ ነበር የሚቀረው፡፡ከተሸሸኩበት ሳልወጣ ልክ ፊልም ላይ ደጋግሜ እንደማየው የያዝኩትን ሽጉጥ ቃቃ አድርጌ በማቀባበል እጄን ወደፊት በግንባሩ አቅጣጫ ቀስሬ ‹‹ ግንባርህን እንዳልፈረክሰው ባለህበት ቁም…››
ስለው ሳያቅማማ ደንዝዞ ትዛዜን አከበረ…እሱ ብቻ ሳይሆን ሶስቱም ያልጠበቁት ስላጋጠማቸው በሉበት ሲርበተበቱ በሰከንድ ሽርፍራፊ ቃኘው …ብዙም ልምድ የሌላቸው የመንደር ሌቦች መሆናቸውን ወዲያው ተረዳው፡፡
አናቴን እያሰራት ወደነበረው ሽጉጡን አዙሬ …‹‹እናቴን ልቀቃት…››ጮህኩበት …
ማሰሩን አቁሞ ቁጢጥ ካለበት በመነሳት ቀጥ ብሎ ቆመ…
ትዕዛዜን ቀጠልኩ ‹‹…አሁን አንድ ሰው ከመግደሌ በፊት እቃውን አስቀምጣችህ እቤቱን ለቃችሁ ውጡ ››
ተያዩና በምልክት በመነጋገር ወደኃላ መሳብ ጀመሩ…በራፍን ካለፉ ቡኃላ በሩጫ አስነኩት…
ከእውነተኛ ሽጉጥ ጋር በእጅ ካልያዙት በስተቀር ምንም ልዩነቱ የማይታወቀውን ልጅ ሆኜ የተገዛልኝን መጫወቻ ሽጉጥ መሬት ጥዬ ወደእናቴ ተንደረደርኩና አፎ ውስጥ የጠቀጠቀውን ጨርቅ ቀድሜ አውጥቼ በመጣል…. እጆቾን ልፈታ ስጣጣር እሷ እልልታዋን እስነካችው…
-እንዴ ምን እየሆነች ነው…?፡፡ግራ ገባኝ፡፡ ሰው እቤቱ ሌባ ሲገባበት ኡኡ ነው ማለት ያለበት ወይስ እልልል….…?
ወይ ድንጋጤ
- …እማ አይዞሽ ተራጋጊ …በማለት እጆን ፈትቼ ስጨርስ ተጠምጥማብኝ እያገላበጠች ትስመኝ ጀመረች
‹‹አደረከው..ልጄ አደረከው….አንድ ቀን እንዲህ እንደሚሆን አምን ነበር…እግዚያብሄር ሁሌም ካንተ ጋ ነው…አዎ አንተ ልዩ ነህ፡፡››
‹‹እማ ..አዎ ደርሼልሻለው … ከአሁን ወዲህ አይኔ እያየ ማንም ሊያጠቃሽና ሊያመናጭቅሽ አይችልም.. ማንም እንደዛ እንዲያደርግ አልፈቅድለትም…››ፎከርኩ
‹‹ እሱ አይደለም ልጄ …እሱ አይደለም..መናገር ቻልክ..ተናገርክ..እያወ
ራሀኝ ነው››ስትለኝ ድንግርግሬ ወጣ….እንዴ እያወራው ነው እንዴ ….…?.ከመገረሜ ሳልወጣ የእናቴን እልልታ የሰሙ የቤታችን ተከራዬች አያቴም ጭምር ከሚጣፍጥ የለሊት እንቅልፋቸው ተነስተው በመምጣት ወደቤታችን ሲንጋጉ ሰማን….

💫ይቀጥላል💫

የኛ ክፍያችን የናንተ ደስታ ነው ስሜታችሁን Like 👍👍 በማድረግ ግለፁልን

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍4
#ሰፊ_ሀገር_ጠባብ_ዜጋ

ሀገሬ ሰፊ ናት ከአድማስ አድማስ የራቀች
ሀገሬ እሩቅ ናት ከሰማየ ሰማይ የመጠቀች
ሰማይ ናት ሀገሬ የከዋክብት አድባር
ሰማይ ናት ሀገሬ የመላእክት ሀገር
#ሌላም
ሀገሬ ሳሌም ናት የአዳም መሰረቱ
የተፈጠረባት መገኛ የጥንቱ
የሰው ዘር ያለባት ደግሞ እንስሳ አውሬ
ጥርት ኩልል ያለች መሬት ናት ሀገሬ
የሚመግብባት አብርሃም ታላቁ
ፀሐይ ያቆመባት ኢያሱ ምጡቁ
ባህርን ያቆመባት ነቢያችን ሙሴ
ሁሌ ' ሚሰማባት የሰማይ ቅዳሴ
ጻድቃን በስራቸው የሚጠለሉባት
ኀጥአን በስራቸው የሚሰወሩባት
የንጹሀን ሀገር ሀገሬ ኤደን ናት
#ግን
ጠባብ ሰው ገጠማት ሰፊ ሁና ሳለ
ያላየውን ሁሉ የኔ ነው እያለ
ለምለም ሳር እያለ ደረቅ በል እንስሳ
ስጋ ሞልቶ ተርፎ እጸ በል አንበሳ
ውሃ ጠጪ ድመት ወተት ሞልቶ ተርፎ
ቅጠል ለበስ ትውልድ ጥጡ ተረፍርፎ
ሁሉም በዝተው በዝተው ግብራቸው ተሽጦ
ሀገር ጠባብ ሆነች ስሟ ተለውጦ
#ግሩም ነው
ስንት ኪሎ ሜትር የማይመጥናትን
ስንት ስንት ማይል የማይገድባትን
ጠባብ ሰው ለክቷት ስሟም ተቀየረ ቁጥሩ እየባከነ
የአገሬ ስፋቷ ሴንቲ ሜትር ሆነ!!!!
ጠቢብ እስኪፈጠር አስኪታወቅ ልኳ
ለጊዜው ጠባብ ነው የሀገሬ መልኳ

🔘ሞገስ ሁንያለው🔘
👍1
#የመልስ_ጉዞ_ወደ_መነሻ
:
#ክፍል_ዘጠኝ
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ከአስር አመት ቡኃላ ማለቴ አንደበቴ ከተፈታ ቡኃላ ያለኝ ህይወት ከዛ በፊት ከነበረው ፍጽም በተቃራኒ መንገድ የተጓዘ ነበር፡፡
በተለይ አንደበቴ እንዲፈታና እንድናገር ምክንያት የሆነው የቤታችን የመዘረፍ ሙከራ እና እኔ እራሴንም ሆነ እናቴን ከጥቃት የታደኩበት ሁኔታ ቅጽበታዊ የአንድ ቀን ክስተት ብቻ ሆኖ አላለፈም ፡፡የህይወቴን አቅጣጫና መላ አመለካከቴንም ሙሉ በሙሉ ነው የቀየረው፡፡
ሌቦቹ ልምድ ያላቸው ደፋርና ጨካኝ ቢሆኑ ኖሮ የዛን ለሊት እኔና እናቴ አልቆልን ነበር ማለት ነው፡፡ወይ ሞተን ወይ ደግሞ አካላ ጎዶሎ ሆነን ነበር፡፡ከዛ ታሪክ የተማርኩት በዚህ አለም ላይ አሸናፊ ሆኖ ለመኖር ብልህነት ብቻ ሳይሆን የአካል ጥንካሬም ወሰኝ እንደሆነ ነው፡፡
ብዙውን ጊዜ ምሉዕ እና ስኬታማ የሆኑ ሰዎች የአዕምሮአዊና እና የአካላዊ ጥንካሬያቸው ምርጥ በሚባል የብቃት ደረጃ የሚገኝ መሆኑን ታሪክ ይመሰክራል ፡፡ያ መሆኑ ሰዎቹ በሚጓዙበት በህይወት መስመር ላይ የፊት መሪ ሆነው ለመመረጣቸው ባይመረጡም እንኳን እራሳቸውን በራሳቸው መሪ አድርጎ ለመሾም እና ለዛም የሚደግፎቸው በርካታ ሰዎች በዙሪያቸው ማሰለፍ የመቻላቸው ሚስጥር የነፍስ ልህቀት ቅኝታቸው እና የአካል ጥንካሬ ብርታታቸው እኩል ዳብሮ መገኘቱ …በማድረግ ብቃታቸው ላይ ሆነ ሌላው ማህበረሰብ ላይ ተፅዕኖ የማሳደር ሚስጥራዊ ሀይል እንደሚያጎናጽፋቸው ገና በጥዋቱ በአስር አመቴ ተገለፀልኝ፡፡እና ሰፈራችን የሚገኝ ቴኮንደ ማሰልጠኛ ቤት መማር እንደምፈልግ ለእናቴ የነገርኮት ወዲያውኑ ነበር፡፡ለምን ፈለከው . ..?ምን ያደርግልሀል..? ምናምን ብላ ሳትጨቀጭቀኝ..ወዲያው የሚከፈለውን ከፍላ ወስዳ እስመዘገበቺኝ፡፡እናቴ የእኔ ጀግና ፡፡
ታዲያ የዛ ውጤት 15 ዓመት ሲሞላኝ ደረቴ ወደፊት የተገለበጠ…ሆዴ እንደብረት ጠጥሮ ወደ ውስጥ የተጠቀለለ…የእጆቼ ጡንቻዎች ፈርጣማ ..ተፈጥሮ ከለገሰኝ ዘለግ ያለ ቁመት ጋር የሀያ አመት ጓረምሳ አስመስለኝ፡፡በአካልም ሆነ በአዕምሮ ከእኩዬቼ አንፃር በጣም በሚባል ደረጃ ቀድሜ አደኩ፡፡ በዚህ ምክንያት ይሁን በተፈጥሮ ባለኝ መስህብ በእንስቶች የፍቅር እይታ ውስጥ በቀላሉ እገባለው፡፡ይቀርቡኛል …ሊፈትኑኝ፡፡ሸሻቸዋለው… እንዳይጥሉኝ ፡፡
ሌላው ትምህርቴን በተመለከተ በቀላል ልፋት አስደማሚ ውጤት ማምጣት ለእኔ የሚወዱትን አስደሳች የካርታ ጫወታ የመጫወትን ያህል ቀላል ሲሆን ለሌላው ተመልካች በተለይ በቀን ስንት ሰዓት እንደማጠና ..?ምን ስሰራ እንደምውል..? ለሚያውቁ ሰዎች እና ጓደኞቼ አስደማሚ እና ግራ አጋቢ ነበር፡፡
‹በልጅነቱ እናቱ አብሾ አግታው ነው ጎበዝ የሆነው ›ብለው ሚያሙኝ እኩዬቼም ሆኑ የሰፈር አዛውንቶች እንዳሉም አውቃለው፡፡
***
ሌላው ባህሪዬ ከትምህርት ጉብዝናዬ ጋር የማይሄድ የማፊያነት ባህሪ ይታይብኝ የጀመረው ገና በጥዋቱ ነበር፡፡መጀመሪያ በእኔ መሪነት የሚንቀሳቀሱ ሶስትና አራት ልጆችን በማስተባበር ጥቃት የሚደርስባቸውን የሰፈር እና ሌሎች የማቀቸውን ሰዎች ከጥቃት በመከላከል ነበር የጀመርኩት፡፡እያደር ግን በትምህርት ቤቱ ስውር መንግስት ሆንኩ፡፡እኔ ያወጣውትን ህግ እንኳን ተማሪዎች አስተማሪዎች ወደውም ሆነ ፈርተው ይተገብሩታል፡፡
ግን ጉልበት አለኝ ብዬ በመታበይ ከመሬት ተነስቼ ሰውን አልጋጭም፡፡በማንም ላይ ከአስፈላጊው በላይ ጉልበትም ሆነ ጫና አልፈፅምም ፡፡ግን ተገቢውን እርምጃ በተገቢው ጊዜና መጠን ለመውሰድ ሰውዬው ማንም ይሁን ማንም አልፈረምም …ላቅማማምም፡፡
ኃይልን በተመለከተ አንድ ምክር ልስጣችሁ ፡፡የሆነ ስልጣን አለኝ ወይም አስተማማኝ ጉልብት አለኝ ብላችሁ ማንኛውንም የመጨረሻ ደካማ ነው የምትሉትን ሰውም ላይ ቢሆን የመጨረሻ ውን ተስፋ እስኪቆርጥ ድረስ አትቅጡትም … አትግፉትም ፡፡..ያንን ካደረጋቹ የራሳችሁን ጉድጓድ እየቆፈራችሁ መሆኑን እወቁት ፡፡ተስፋ የቆረጠ ድመት የነብር አንገት መቀንጠስ ቢያቅተው እንኳን የነብርን አይን ለማጥፋ አይሰንፍም፡፡
እና ምን ጊዜም ይሄ የሀይል አጠቃቀም ለእኔ መመሪያዬ ነው፡፡ያሸነፍኩትን በምን ያህል መጠን መቅጣትና መቼ ይቅር ማለት እንዳብኝ በጥንቃቄ አስብበታለው፡፡
ያው የትምህርት ቤቱ ስውር መንግስት ነኝ ብያችሁ የለ፡፡መጀመሪያ በዘፈቀደ ነበር ነገሮችን የምከውን የነበረው፡፡ዋናው ትኩረቴ የሆነ ታዛዥ ጦር ከኃላዬ ማሰለፌ እና በሚያውቁኝም (እጄን በቀመሱትም) ወይም በዝና ብቻ በሰሙትም ዘንድ መፈራቴ እና መከበሬ ነበር፡፡
በነገራችን ላይ በሄድኩበት ሁሉ የመከበርና እና የመደመጥ ሱስ አለብኝ፡፡ማንም ቢሆን በእድሜ እኩያዬ ይሁን ወይም ታላቄ ትኩረት እንዲነፍገኝ ወይም ዝቅ አድርጎ እንዲያኝ ፈጽሞ አልፈቅድም፡፡ሲያከብሩኝ ደስ ይለኛል፡፡አዎ ማንኛውም ሰው ከቻለ እየወደደ ቢያከብረኝ ደስ ይለኛል ካልሆነ ግን እየጠላኝም ቢሆን እንዲፈራኝና እንዲያከብረኝ ፈልጋለው፡፡በሚወዱኝም ሆነ በሚጠሉኝ ሰዎች እኩል መፈራትና መከበር ፍላጎቴ ነው፡፡

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
#የቦርሳሽ_ላይ_ስእል
:
ካነገትሽው ቦርሳ ፥ ከጀርባሽ ላይ ካለው
የዚያ ዘፋኝ ምስል ፥ ደምቆ የታተመው
ልብ ብዬ ሳየው ፥ ሁሌም ይገርመኛል
እንደ ኪነት ተውኔት ፥ ማርኮ ያስቀረኛል
:
#ያንን_የጨርቅ_ቦርሳ
በደብተር በመፅሃፍ ፥ የወጠርሽው ለታ
በድምፃዊው ፊት ላይ ፥ ይታያል ፈገግታ!
ባዶ ሲሆን ደ'ሞ ፥ ወይ አንድ-ሁለት ደብተር፤
#ጨርቁ_ተጨማዶ
አያለሁ ስእሉን ፥ ደርሶ ሲኮሳተር !
:
ይህ አይደለም ወይ? የእኛስ ህይወት ዳራ
ሁለት አይነት ምስል ፥ በአንድ የስእል ሸራ!
ትንግርቱ ገፃችን፤
በቀን አስር ጊዜ ፥ ተቋጠሮ 'ሚፈታ
ሲጎድል ትካዜ ፥ ሲሞላ ፈገግታ!!
#የመልስ_ጉዞ_ወደ_መነሻ
:
#ክፍል_አስር
:
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...አደኩ፡፡ጎረመስኩ፡፡ጉንጬ ላይ ብጉር አገጬ ላይ ፀጉር አበቀልኩ፡፡ያንንም ተከትሎ
➶➶➶
ፍቅሬ አስትንፋስህ ህይወቴ ነው፡፡ያንተ መኖር ደግሞ ለእኔ ብቸኛ የመኖር ዓላማዬ፡፡አንተ ፀሀዬ ነህ፡፡ እንጦጦ ተራራ ላይ በበቀለ አረንጎዴ ሳር ላይ በጀርባ ተንጋለው ከጥዋት ሦስት ሰዓት አካባቢ የሚሞቋት ሰውነትን የምታፍታታ፤አዕምሮን የምታነቃቃ፤የቆዳን ቀለም የምታፈካ ምጥን የእግዜር ፀሀይ፡፡ አዎ አንተ እንደዛ ነህ፡፡ሙሉ ፀሀይ ከእነግለቷ፤ ሙሉ ፀሀይ ከነኩነቷ ፡፡ከአንተ ሙቀት ተሸርፎ አኔ ጋር የሚደርሰው ሙቀት ፍፅም ያኖረኛል…ፍፅም ያፈካኛል፡፡
እንደእኔው ፈገግታህን ለማድነቅና ከዛም አለፍ ሲል በሙቀትህ ለመቅለጥ በመፈለግ በየእለቱ በዙሪያህ ሲያንዣብቡ የሚውሉ የትምህርት ቤታችን ቆነጃጅቶች እንዳሉ አውቃለው፡፡ግን ደግሞ አንዳቸውም በእኔ መጠን ውብ እንዳልሆኑ በእኔ መጠንም አንተን አንደማያፈቅሩ በእርግጠኝነት አውቃለው፡፡ባውቅም ዳሩ ተረጋግቼ መቀመጥ አልቻልኩም ፡፡..ልቤ በቅናት ያራል….ውስጤ እርብሽብሽ ይላል፡፡አንዳንዴ የሆነ ሽጉጥ ፈልጌ በእየእለቱ አንትን በሙሉ አይኗ ለማየት የምትደፍርን ማንኛዋንም ልጅ-አገረድ ግንባሯን ብቀነድባት ደስታዬ ነው፡፡ግን ያንንነ ለማድረግ ችሎታውም ሆነ ድፍረቱ ለጊዜው የለኝም፡፡በቅርብ ግን አምላክ ኃይሉን እንደሚያጎናፅፈኝ አምናለው..እናም የዛን ጊዜ አደርገዋለው፡፡ለአንተ ስል ከተማ አቃጥላለው፤ ለአንተ ስል ሺ ሰው ገድላለው…ለአንተ ስል እራሴን ከ20 ኛው ፎቅ ላይ ልወረውርም ችላለው…ለአንተ ስል የማላደርገወ ነገረ የለም…አስፈላጊ ከሆነ ለአንተ ስል አንተ ራስህንም መግደል ችላለው፡፡
ጊዜው ደርሷ ሁሉን ማድረግ እስክችል ግን አንተን የመጠበቅ አደራውን ለአንተው ለራስህ ሰጥቼያለው፡፡ የእኔ ጀግና ሴቶችን በተመለከተህ ባለህ አቋም ታኮራኛለህ እናም በዚሁ ቀጥል፡፡ ለአንዳቸውም ፊት አትስጣቸው፤ለአንዷም የልብህን ወርቃማ በር አትክፈትላት…የትኛዋም ብትሆን በብሩህ አይኖችህ አይታ ውስጥ አትግባ…ክንዶችህ የማንኛዋንም ወገብ ለማቀፍ አይሞክሩ …ወለላ ማር የሚንጠባጠብባቸው ሚመስሉ ከንፈሮችህ የማንኛዋም ቆርፋዳ ከንፈር ላይ አይረፍ …ቅዱስ ትንፋሽህን የትኛዋም ሄዋን ከእራሷ ሙትና ደካማ ትንፋሽ ጋር ቀይጣ ወደውስጦ ለመሳብ እድል አታግኝ ፡፡…በማንም ሴት ቀልድ ጥርሶችህ ተፈልቅቀው ፈገግታህ እንዳይረጭ…፡፡ለአንተ የምገባህ እኔ ነኝ..ከጎንህ አጥንት ተፈልቅቄ የተፈጠርኩ ሄዋንህ…ብትረግጠኝ ማይቆረቁረኝ፤ ብትገለኝ ቂም ማሊዝብ፡፡ብታቅፈኝ ማልጎረብጥህ ብትሰመኝ የማስደስትህ፡፡እኔ ለአንተ ጌጥህ እኔ ለአንተ ክብርህ ነኝ …፡፡በፈለከው ደቂቃ ጥራኝ በርሬ ወዲያው መጣለው፡፡ያሰኘህ ቦታ ቅጠረኝ ሲኦልም ቢሆን እገኛለው፡፡ ………..
***
ይሄ አስራ አምስት አመትና የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ እያለው ከክፍሌ ልጅ የተፃፈልኝ የመጀመሪያው የፍቅር ደብዳቤዬ ነው፡፡ከዛ ቡኃላ ያለውን የአፍላነት የፍቅር መሳሳቡንና የስሜት መላተሙን አትጠይቁኝ ፡፡ ይሄንን ለእናንተ እንደምሳሌ መናገር የፈለኩት እያደኩ ስመጣ ምን ያህል ማራኪ ወንዳ ወንድ እና ተፈቃሪ ወጣት መሆኔን እንድትገዘቡልኝ ስለፈለኩ ነው።

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍4
#በኔ_ቤት
:
በኔ ቤት……
ፍየል ቅጠል አይታ፤ሳትበላ ታድራለች
ዶሮ ጥሬ ረግጣ፤ልፆም ነው ትላለች
ውሻ ስጋ እያየ፤በረሀብ ይሞታል
ሰው እህል ቀርቦለት፤ባዶ ድስት ይከፍታል


#በኔ_ቤት

አንበሣ ሚዳቋን፤አቅፎ ይስማታል
ጅብ ስጋ ላይበላ፤ምሎ ይገዘታል
ዕባብ ሰውን አይቶ፤አይተናኮልም
ነብር ጎሽ አይጥልም


#በኔ_ቤት

አንድ ብር ላይ ያለው
ትንሹ እረኛ መሳቁን ያቆማል
የሰፌዱም ስፌት፤ሳንቲም ላይ ይሆናል
ወተት የጠጣ ህፃን፤ሰክሮ ተንገዳግዶ
የአስር ዓመት ልጅ፥አስር ልጆች ወልዶ
የሰፈር አዛውንት፥ሰፈር ይቦርቃል
ሩቅ ያለው ቀርቦ፥ቅርብ ያለው ይርቃል


አሁንም…
ከጣልሺኝ ቦታ ላይ፤ብቻዬን ቁጭ ብዬ
ታምራዊ ስዕል፤በአይምሮዬ ስዬ
ሀሳቤን ጥጃለሁ፥ማይበስል ማይመስል
ዳግም በህይወቴ፥አገኝሽ ይመስል

🔘ልዑል ሀይሌ🔘
👍3
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ_ጉዞ
:
#ክፍል_አስራ_አንድ
:
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...18 ዓመት ወጣትና የ12 ክፍል ተማሪ ሆኜ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለኝን ማትሪክ ፈተና ዝግጅት ላይ እያለው አስቀያሚ ነገር ተከሰተ፡፡አስቀያሚ ስላችሁ የመጨረሻ አስቀያሚ ማለቴ ነው፡፡ትምህርት ቤት ክፍል ውስጥ ቁጭ ብዬ በማማር ላይ ሳለው በስልኬ መልዕክት መጣ ፡፡ሳየው ከአያቴ ነው፡፡ያልተለመደ ነገር ነው፡፡የሚያስተምረውን አስተማሪ ትኩረት እንዳልስብ እየተጠነቀኩ ከፈትኩና አነብኩት….ደብተሬን እንኳን አልሰበሰብኩም፡፡ ተስፈንጥሬ ከመቀመጫዬ ተነሳው ፡፡ የክፍሉ ተማሪ አይን ከአስተማሪው ተነቅሎ ወደእኔ አነጣጠረ..አስተማሪው ማስተማሩን አቋርጦ ምን እንደሆንኩ መጠቅ ጀመረ …እየተንደረደርኩ ክፍሉን ለቅቄ ወጣው፡፡ሳይክል ሚጠቀሙ ተማሪዎች ሳይክላቸውን ወደሚያቆሙበት ስፋራ ነው የሮጥኩት፡፡ከመካከሉ ቁልፉ ያልተቆለፈውን አዋጣውና እየጋለብኩ ግቢወን ለቅቄ ወጣው፡፡ ሳይክሉ የማን እንደሆነ አላውቅም ግድም አልነበረኝም..
ሆስፒታል እንደደረስኩ ሳይኩል ወረድኩና ከመንገድ ዳር አጋድሜ ወደውስጥ ሮጥኩ… ኮሪደር ለኮሪደር እየተሸከረከርኩ አያቴን ወይንም ሌላ የማውቀው ሰው መፈለግ ጀመርኩ...አዎ አያቴን አገኘውት
-እናቴ የታለች …?እናቴ ምን ሆነች…??እማ!!
ተረጋጋ…ምን እንደሆነች አናውቅም…ድንገት ነው እራሷን የሳተችው ፡፡እያከሟት ነው፡፡ይውጡና ሚሉትን እንሰማለን፡፡››አለኝ አያቴ በሚርበተበት ድምፅ..
‹‹እራሴን መቆጣጠር አቃተኝ፡፡‹‹ቆይ አያቴ እንደዚህ አይነት ነገር እንዴት ይፈጠራል …?እናቴ ፍጽም ጤነኛ ነበረች፡፡እንኳን እራስ መሳት ይቅርና እራሷንም ሲያማት አይቼ አላውቅም ፡፡››
‹‹ለእኔም አንቆቅልሽ ነው የሆነብኝ ልጄ››አየቴ መለሰልኝ
ንግግሬን ሳልጨርስ እናቴ ስትታከምበት ከነበረው ክፍል አንድ ዶክተር ወጣ… ተንደርድረን ከበብነው፡፡ዶክተሩ እኔንና አያቴን ወደቢሮ ይዞን ሄደ፡፡ ካዘነው በላይ የሚያሳዝን …ከደነገጥነው በላይ የሚያስደነግጥ መርዶ ነገረን፡፡
‹‹የሚቀጥሉትን ሶስት ቀን እዚህ ትቆይና …ከዛ ትወስዶታላችሁ››
‹‹ተመስገን›› አለ አያቴ …ረጅም ግን ደግሞ ደካማ ትንፋሽ ተንፍሶ፡፡
‹‹ዶ/ር በሶስት ቀን ይሻላታል ማለት ነው…?››ጠየቅኩት በመፍለቅለቅ ….ለማረጋገጥ፡፡
ዶክተሩ አንገቱን እንደመድፋት አለና የተወሰነ አየር ወደውስጡ ስቦ ጭንቀት በሚለቅ ድምጽ ‹‹አዝናለው ..ይሻላታል ብዬ ተስፋ ልሰጣችሁ ብችል ደስ ይለኝ ነበር…ግን እሷን የማዳኑ ጉዳይ ረፍዶብናል››
‹‹ማለት …?››
እቤት ወስዳችሁ ያላትን ቀሪ አንድ ወርም ሆነ ሁለት ወር በደስታ አሳልፋ …በሰላም እንድታርፍ ከማድረግ ውጭ ሌላ ምርጫ የላችሁም፡፡››አለ የመለማመጥ ቃና ባለው ድምፀት፡፡
ከመቀመጫዬ ተንሳፍፌ ተነሳውና የሸሚዝኑን የጋወኑን ኮሌታ አንድ ላይ ጨምድጄ ከተቀመጠበት አንጠልጥዬ አስነሳውትና በአየር ላይ አንሳፍኩት…ሰውዬው አይኑ ተጉረጠረጠ..እጆቹን እንድለቀው ማወራጨቱን ቀጠለ
አያቴም ከድንዛዜው እንደምንም ባኖ ይለምነኝ ጀመር
‹‹ልጄ ምን እየሰራህ ነው..…?ሰውዬውን ልቀቀው..…?ልጄ የሰው ሰው እንዳትገል፡፡››
‹‹እናቴን ታድናታለህ አታድናትም.…?››አርገፍግፌ መሬት አድርሼ ለቀቅኩት
ዶክተሩ ጉሮሮውን በእጆቹ እየዳበሰ ደጋግሞ ካሳለ ቡኃላ‹‹.አዝናለው አልችልም…ማንም ሊያድናት አይችልም….››ብሎ ስለበሽታዋ አይነትና ከባድነት የደረሰበትን ደረጃ በተቆራረጠ ቃላት ይዘረዝርልን ቀጠለ.
በእናቴ ስም እምላለው…ከሞተች አገድልሀለው..አንተን ብቻ ሳይሆን ጠቅላላ እዚህ ግቢ ውስጥ ያላችሁትን ሀኪሞች ጨርሳችሆለው …ሆስፒታሉንም አቃጥለዋለው፡፡አረ ከተማወናም ነው የማቃጥለው…››በማለት ቢሮውን ጥዬ ወጣውና እናቴ ወደተኛችበት ክፍል ተንደረደርኩ ፡፡በራፍ ላይ የቆመችውን ነርስ ገፍቼ ፍቃዷንም ሳልጠይቅ ወደውስጥ ገባው፡፡እማዬ ዝርር ብላ ተሰትራ የሆስፒታሉ አልጋ ላይ ተኝታለች፡፡አይኖቾ ተከድነዋል፡፡ትንፋሿም አይሰማም ፡፡በሁለቱ አፍንጫጮ ቀዳዳ ቱቦ በክንዶቾ የግሉኮስ ላስቲክ ተሰክቶል፡፡
በራስጌዋ ሄድኩና ወለሉ ላይ ዝርፍጥ ብዬ ግንባሬን አልጋዋ ላይ ደፍቼ ወደ ፊቷ ተጠግቼ አስደገፍኩና በሹክሹክታ አወራት ጀመር….
ማሂ ምን እየሰራሽ ነው…?፡፡ምንድነው ዶክቱሩ የሚቀባጥረው…?፡፡ጥላህ ልትሄድ ነው እያለኝ ነው፡፡ስለማያውቅሽ ነው የሚቀባጥረው ፡፡አንቺ መቼም መቼም እኔን ጥለሽ መሄድ እንደማትችይ ስለማያውቅ ነው፡፡ገነትም ቢሆን እኔ ከሌለው መኖር እንደማትችይ ስለማውቅ ነው፡፡ማሂ ከተወለድኩበት ቀን አንስቶ ስትበይ እንብላ ብለሺኝ ስትተኚ እንተኛ ብለሺኝ ፤ስትተነፍሺ እንኳን የእኔንም መተንፈስ አረጋግጠሸ ነበር…ታዲያ ዶክተሮቹ እንደሚሊት አሁን ልትሞቺ ከሆነ እንዴት ልንሞት ነወ ተዘጋጅ ሳትይኝ .. …?ነገሩ ተይው እውነት ዶክተሩ አንዳለው ሸውደሺን ለመሞት የተዘጋጀሽ ከሆነም ግድ የለም እኔ ዝግጅት አያስፈልገኝም፡፡
ንግግሬን ከጀርባዬ ሆኖ ሲያዳምጥ የቆየው አያቴ በሽማግሌ አንጀቱ እየተንሰቀሰቀ በማልቀስ ዝቅ ብሎ አስነሳኝና
‹‹ተው ልጄ ተረጋጋ…አይዞህ እግዜር አለ ያድንልናል፡፡››
እንግዲህ እግዚያብሄር አለ የምትል ከሆነ በምትግባቡበት ቋንቋ ንገረው…ተው የሰው እናት አትንጠቅ በለው…እሷን አጥቶ መኖር አይችልም በለው…ከሰማህ ጥሩ ነው ፡፡ ካልሰማህ ደግሞ እኔንም ተሰናበተኝ ፡፡ እናም ከእናቴ ጋር በአንድ ጉድጓድ መቀበር ነው የምፈልገው..እንዳትረሳ በአንድ ጉድጓድ ፡፡ይህ ኑዛዜዬ ነው፡፡››ብዬው ጥዬው ወጣው ፡፡ወደየት እንደምሄድ ባላውቅም የሆስፒታሉን ቅጥር ጊቢ ለቅቄ ወጣው….

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍42
#ስንቴ_ገረዝኩት✂️
:
#ክፍል_አንድ
:
:
ደራሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
“አንቺማ አትገርዢኝም። በስመአብ! ” አለ እያማተበ ለመቀመጥም ለመነሳትም በቀረበ አኳኋን አየሩ ላይ ተንጠልጥሎ።
“አየር ላይ ነህ፣ አረፍ ትል?” አልኩት አኳኋኑ ሳቄን እያመጣው
“የታለ ዶክተሩ ከምር? ” አለኝ ወንበሩ ላይ ተስተካክሎ እየተቀመጠ
“እኔ ነኝ!!” አልኩት ምን እንደሚያስብ ለመገመት እየሞከርኩ
ካርዱ ላይ የተፃፈው እድሜ 33 ይላል። ወጣት ነው፣ ማንም ሴት አይታው የምትደነግጥለት ዓይነት ቁመናና መልክ፤ በራሱ የሚተማመን የሚመስል ገፅታ ፤
“አንቺማ አትገርዢኝም። ይዤው አረጃታለሁ እንጂ………” አለኝ ለኔ ሳይሆን ለራሱ የሚያወራ በሚመስል ድምፅ
“ለምን? ሴት ስለሆንኩ?”
“አወና ፣ ሴት ብቻ አይደለሽም። ህልም የመሰልሽ ቆንጆ ሴት ነሽ። ሆ!!”
“እሱ ከስራዬ ጋር ምን አገናኘው?”
“ላንቺ ነዋ ስራ…………” ቀጥሎ ያልሰማሁትን ነገር አጉተመተመ
“ይቅርታ አቶ ሲሳይ ብዙ አገልግሎት ፈላጊዎች ውጪ ተሰልፈዋል። ስራችንን እንቀጥል?”
“እህ ስለተቆጣሽ ይሰማሽ መሰለሽ እንዴ?” አለ ወደሱሪው ዚፕ አይኑን እየላከ። መሳቅ አምሮኛል ግን መሳቅ የለብኝም።
“እንዴት ሳትገረዝ ……….?” ጥያቄዬን የምጨርስበት ቃል ስፈልግ
“አረጀህ? አይባልም ግን እሺ! ……….. ባክሽ አንጀት ነው ታሪኩ። ………… ተረት ነገር ነው የሚመስለው።”
“እየሰራሁ ታወራኛለሃ!!”
ብድግ ብሎ ገላውን አራቆተው።
“እንዴ እዚህ አይደለም የምሰራው።።።” አልኩት
“ቆይ ግን ትልቅ ወንድ ገርዘሽ ታውቂያለሽ?” አለኝ ምንም የተጋለጠ ሳይመስለው ተረጋግቶ ልብሱን ወደሰውነቱ እየመለሰ።
” አዎ። አውቃለሁ። ”
“እኔን የሚያህል?”
” ካንተም የሚበልጡ”
“ይሄን ነገር መቼም እንዲህ እንደቆመ አትገዘግዢውም አይደል?” እፍረት አይታይበትም። ስለቆመው አክሱም እንጂ ስለቆመው ንብረቱ ያወራ አይመስልም። በድጋሚ መሳቅ አምሮኛል። ፊቴን አዙሬ ፈገግታዬን ደበቅኩበት። ጭንቅላቴ ውስጥ ብቅ ያለው ሀሳብ ግን ቆሞ ነበር እንዴ? የሚለው ነበር። በየሱስ ስም!
“ማደንዘዣ እሰጥሃለሁ።”
“እህ! አይደለም ማደንዘዣ ፀሀይ የመሰልሽ ሴት ነክተሽው ሞቼ እንኳን ቢሆን አይቆምም?”
አሁን አለመሳቅ አልችልም ነበር። መጥሪያዬን ተጭኜ እጄን ከማንሳቴ ሲስተር ገባች።
“ኸረ ፍጥነት? በሩ ላይ ነበረች እንዴ? ” በማያገባው የሚገባ ሰው በቸልታ ማለፍ አልችልም እኮ ግን እንዳልሰማ ወደ ሲስተር ዞርኩ
”OR 2 ይዘጋጅልኝ። ማረፊያውን ታሳይሃለች እዛ ቆየኝ።” ካርዱን ለሲስተር አቀበልኳት። እሷ ያልኳትን ሰምታ ወጥታለች። እሱ እንደተቀመጠ በትዝብት ያየኛል።
“ምንድነው?”
“ይሄን ፊትሽን ግን ስሞትልሽ ፀብ ሲኖረኝ ሲኖረኝ እዋስሻለሁ። እንቢ እንዳትዪኝ! ኸረ በኪዳነምህረት!! “
“አቶ ሲሳይ የሚመለከተን ነገር ላይ ትኩረት እናድርግ?“
“you see እያናደድኩሽ እንኳን ፈገግ ብለሽ ነው የምትቆጪኝ። ምክንያቱም ደሞዝሽን የምከፍልሽ እኔ ነኛ! ባትመቺኝ ሌላ አማራጭ እንደምጠቀም ታውቂያለሽ። ስለዚህ ምን ያህል ስድ የሆነ costumer እንኳን ቢገጥምሽ በትህትና ታስተናግጃለሽ። ረዳቶችሽ ወደውሽ እንጂ ደመወዝ ስለምትከፍያቸው ፈርተውሽ እንዲታዘዙሽ አታድርጊ! እንደዛ ሲሆን አብረውሽ ያሉት ምርጫ እስካጡ ድረስ ብቻ ነው ማለት ነው።”
ልለው ያሰብኩት ብዙ ነበረ። ዋጋ ያለው ስላልመሰለኝ ተውኩትና እንዲወጣልኝ ብቻ በሩን አሳየሁት። ተነስቶ እየወጣ በሩን ተደግፎ ቆም አለና
«ያንቺን ስራ ደመወዝ ከፍለሽ እንደምታሰሪያቸው ሳይሆን እነርሱም የስራው አካል እንደሆኑ እንዲሰማቸው አድርጊ ያኔ ላንቺ ወይ ለደሞዝ ብለው ሳይሆን የራሳቸው ስራ መሆኑን ስለሚያስቡ ማንም ስራው እንዲበላሽበት አይፈልግም።»
«አቶ ሲሳይ ስድስት አመት ይሄን ሆስፒታል ቀጥ አድርጌ አስተዳርያለሁ። ሰራተኞቼን እንዴት መያዝ እንዳለብኝ አንተ አትነግረኝም!!» እንዴት ያለው ነው? እያናደደኝኮ ነው። ፈገግ ብሎ ከወጣ በኋላ መለስ ብሎ
«አይባልም ግን እሺ! ቤት ውስጥ የተቀጠረ ሰው እንኳን አሁን ቀርቷል ሰራተኛ አይባልም። ሆስተስ፣ አቀናባሪ ምናምን ነው የሚባለው። በሙያቸው የሚረዱሽን ሰዎች ሰራተኞቼ? ኸረ አይባልም!» ብሎኝ በሩን ዘጋው!! ኡፍፍፍፍፍፍፍፍ ምን አይነቱን ነው ዛሬ ደግሞ የጣለብኝ?
★ ★ ★
በሶስት ቀናት ውስጥ የተኛሁባቸው ሰዓታት 7 መሙላታቸውን እንጃ። እቤቴ ሄጄ አላውቅም። ተረኛ ታካሚ እስኪገባ ስጠብቅ እያወራ ወደ ውስጥ ዘለቀ።
“ስንቴ ነው የምትገርዢኝ?”
“ማለት?”
“ቁስሉ ተቦትርፎልሻል። ጨርሺኝ ብዬ ነው አንቺውጋ የመጣሁት።”
“አልገባኝም። እስኪ እዛጋ ሁንልኝ። ምን ሆኖ ነው?” አልኩት
“እኔ አንቺን ማሰብ ማቆም አቃተኝ። እሱም አለመቆም አቃተው። ተነፋፋሁ ሲል ቁስሉ ጣጣጣ…………” የሚያሾፍ ይመስላል። ቁስሉ ግን እንዳለው ቆስሎ ነበር።
“ስነስርዓት ባለው መንገድ እንደአዋቂዎች እናውራ?” አልኩት።ማንም ደንበኛ በዚህ መጠን ነፃነት እንዳወራኝ አላስታውስም።
“እኔ የምለው ማሂ?” አለ ኮስተር እንዳለ
” ዶክተር ማህደር” መለስኩለት
“ኡፍ! ከክብርና ከፍቅር የቱ ይበልጥ ይመስልሻል?”
“ሁለቱም ዋጋ ያላቸው የማይነፃፀሩ ነገሮች ናቸው።”
” ዶክተር ብልሽ ያከበርኩሽ ሊመስል ይችላል። ማሂ ስልሽ ግን ውዴታዬን እየነገርኩሽ ነው። ከክብር ሁሌም ፍቅር ይበልጣል። በክብር ውስጥ ፍቅር ላይኖር ይችላል። በፍቅር ውስጥ ግን ሁሌም ክብር አለ” የሆነ ነገሬን ያወቀ ስለመሰለኝ ተናደድኩ። ለተናገረው ትኩረት የሰጠሁ ባለመምሰል
“ጨርሻለሁ። ተጨማሪ አንድ መድሀኒት አዝልሃለሁ። በትክክል መድሀኒቱን ከወሰድክ በድጋሚ እዚህ መመላለስ አያስፈልግህም።” አልኩት
” OK አልጋ ልትሰጪኝ ማለት ነው? እሱ ጥሩ ሀሳብ ነው። ”
“አቶ ሲሳይ ለጨዋታ ጊዜ የለኝም።”
” ሊኖርሽ ግን ይገባል ማሂ!። ” መልስ ሳይጠብቅ የፃፍኩለትን ወረቀት ተቀብሎኝ ወጣ።

⚫️ይቀጥላል⚫️

ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳችሁ Like 👍 እያደረጋቹህ ምርጦቼ😘

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍91
#ስንቴ_ገረዝኩት ✂️
:
#ክፍል_ሁለት
:
:
ደረሲ:-ሜሪ ፈለቀ
:
:
....“ዶክተር? ያው ሰውዬ ነው የላከልሽ………” ሲስተር ቀለም በፈገግታ በደመቀ ፊት ጠረጴዛዬ ላይ በፎይል የተጠቀለለውን ምሳ አስቀምጣው ወደ በሩ ተመለሰች
“ሲስተር ከዛሬ በኋላ የሚያመጣውን ምሳ እንዳትቀበሉት።” አልኳት
ለሁለተኛ ጊዜ ታክሞ ከሄደ ጀምሮ ሶስት ቀኑ ነው። የምሳ ሰዓት እየጠበቀ ምሳ ይልካል። ጠዋት ፅዳቶቹ አፅድተው ሲጨርሱ አበባ ይልካል።
“አበባውንም ነው ዶክተር?”
“አዎን። ምንም ነገር!!”
“እሺ!!” ብላኝ ወጣች
ሲስተር ለምንድነው የምትሽቆጠቆጥልኝ? ስለምታከብረኝ? ደሞዝዋን ስለምከፍላት? አለቃዋ ስለሆንኩ? እንጂ አትወደኝም…………… ትጠላኝም ይሆናል። ይሄ የተረገመ ሰው ምን እንዳስብ እያደረገኝ ነው?
★ ★ ★
ሆዴ ምግብ አስፈልጎታል። ሆስፒታሉ አቅራቢያ ያለ ሬስቶራንት እራቴን ለመብላት አዝዤ ተቀምጫለሁ። ከየት መጣ ሳልል ከፊቴ ያለውን ወንበር ስቦ ተቀመጠ።
“ማሂ……ዬ……… ?” አለ በተሟዘዘ አጠራር
“አንተ ሰው ለምን አትተወኝም?”
“አቶ ሲሳይ ታፈሰ። ማዕረግ ያለኝ ሰው ነኝ እሺ።”
“Whatever አቶ ሲሳይ ምን እያሰብክ እንደሆነ አልገባኝም። እኔና አንተ ግን ምንም መሆን የምንችል ሰዎች አይደለንም።”
“ምክንያት? በእድሜ ስለምትበልጪኝ?”
“አቤት? ”
“በ18 ዓመትሽ ዩንቨርስቲ ብትገቢ፣ 7 ዓመት ዶክተር ለመባል ብትማሪ……”
“ዶክተር ለመሆን ” አቋረጥኩት
“ስፔሻሊስት ለመባል የሆነ ዓመት… …… ይሄን ሆስፒታል ከከፈትሽ 6 ዓመት… …… በስሱ 37 የግልሽ ነው። ”
እንዲያውቅብኝ ባልፈልግም ተናድጃለሁ። ለምን ተናደድኩ? ትክክለኛ እድሜዬን ስለነገረኝ። እና ምን አናደደኝ? ምክንያት እንኳን የለኝም።
“ቁስልህ ዳነልህ?” ወሬውን መቀየር ነው ፍላጎቴ
“እየደረቀ ነው። ላሳይሽ?” ከመቀመጫው ብድግ አለ
“ኸረ አንተ ሰው?” ለመቀመጥም ለመነሳትም በቀረበ አኳኋን አየሩ ላይ ተንሳፈፍኩ
“አየር ላይ ነሽ! አረፍ ትዪ……” ብሎኝ ተመልሶ ተቀመጠ
ያዘዝኩት ምግብ መጣ። ተነስቶ እጁን ታጥቦ እስኪመጣ ጠብቂኝ ባይለኝም ጠበቅኩት። የጠቀለለውን ሊያጎርሰኝ ዘረጋ
“ጉርሻ አልወድም።” አልኩት
“እንዴ? በሞቴ? በፍቅራችን?” ሆነ ብሎ ሬስቶራንት ውስጥ ያለው ሰው እንዲሰማ ጮክ ብሎ ነው የሚናገረው። ሰዎች እየዞሩ ያዩናል። ግማሾቹም ፈገግ እንደማለት ይላሉ። ጎረስኩለት።
“ማሂዬ ለክብርሽ ይሄን ያህል አትጨነቂ። ……” አለ የተናገረው ተራ ነገር እንደሆነ ሁሉ ለሌላ ጉርሻ እየተሰናዳ። ተበሳጭቻለሁ። ይበልጥ ያበሳጨኝ ደግሞ ያለው እውነት መሆኑ ነው።
“ክብር አንጃ ግራንጃህን ተወኝ። ባለትዳር ነኝ ለባለቤቴ …………”
ሳቁ አቋረጠኝ። አስቂኝ ተረት እንደነገሩት ህፃን ተንፈቀፈቀ::
“ምን ያስቅሃል?”
“ባለቤትሽ ነዋ ያሳቀኝ ሃሃሃሃ ”
“ምን ለማለት ፈልገህ ነው?”
” እንዳንቺ አይነት ሴቶች ወይ አላገቡም፣ ወይ አግብተው ፈተዋል፣ ወይ ከባላቸው ጋር ሰላም አይደሉም።”
“እኔ ምን ዓይነት ሴት ነኝ?”
“ካልኳቸው ምድብ ውስጥ ከሌለሽ ልቀጣ? እ?” መልሴን ጠበቀ
መልስ አልነበረኝም። ተነስቼ ጥዬው መሄድ ነበር ፍላጎቴ እግሮቼን ማዘዝ አቃተኝ። ሽንፈቴን መቀበልም መሰለኝ። ልከራከረውም አቅሙ አልነበረኝም።
“እኔ ምን አይነት ሴት ነኝ? ” ድምፄ የቅድሙ ጥንካሬ የለው
“እውቀትና ደረጃዋን ድክመትና ሽንፈቷን ለመሸፈን የምትጠቀም ዓይነት ሴት”
ከዚህ በላይ መስማት የሚያሳምመኝ መሰለኝ። ተነስቼ ስወጣ ድምፁ ተከትሎኛል።
“አየሽ አንቺ ይህቺ ነሽ። ትፈረጥጫለሽ።”
እኔ ምን አይነት ሴት ነኝ? የትኛውን ሽንፈቴን ነው በደረጃዬ የሸፈንኩት?
★ ★ ★
ወትሮም ለእንቅልፍ እምብዛም የሆነው ዓይኔ ጭራሽ አልከደን አለ። እቤቴን ጠላሁት። ልብሴን ለመቀየር ካልሆነ በቀር አዳሬም ሆስፒታል ከሆነ ሰነባበትኩ። ምግቤንም የምመገበው እዛው እያስመጣሁ ሆነ። ከዛ ቀን በኋላ ሲሳይን አላገኘሁትም። ከዛ ቀን በኋላ ግን ስላወራናቸው ነገሮች አለማሰብ አቃተኝ። ሁኔታዬን ይብስ ያባባሰው ደግሞ ከቀናት በፊት የገጠመኝ ነገር ነው። ዶክተር ሰይፈ!!! በግምት የ12 አመት ልጅ የምትሆን ህፃን በዊልቸር እየገፋ ሲያልፍ ነበር ያየሁት። ደሜ ሰውነቴ ውስጥ ሲቀዘቅዝ ታውቆኝ ነበር።
«ሲስተር? ዶክተር ሰይፈ ልጅ አለው እንዴ? » ቢሮ እንደገባሁ ጠየቅኳት። ጥያቄዬ ይሁን ሰይፈ የትኛው መሆኑ ግራ ያጋባት አልገባኝም። « ዶክተር ሰይፈ የህፃናት……………»
«እኮ ገብቶኛል። መጠየቅሽ ገርሞኝ ነው። አዎን ሁለት ሴት ልጆች አሉት። አንዷ ልጁ የመኪና አደጋ ደርሶባት she is totally paralyzed እሱ ነው የሚንከባከባት። አይኗም የማየት አቅሙ እየተዳከመ ነው።» አነጋገሯ ውስጥ ያለው ድምፀት ያሳምማል። አንቺ ምን ግድ አለሽ አይነት ነው።
« ሚስቱስ?»
«ህምምም……. ሚስቱ እኮ ሞታለች ዶክተር!»
« ለምን አልነገራችሁኝም? እንዴት አንድ ሰው አይነግረኝም?» ፀፀቴን ማራገፊያ አጥቼ እንጂ እሷ ላይ የምጮህበት ምክንያትም መብትም የለኝም።
« ምን ብለን? ዶክተር አንቺ ልብ ስለማትዪ እንጂ እኮ ለህክምና እዚህ ትመላለሳለች።» ብላኝ በመገረም እያየችኝ ወጣች።
ኡፍፍፍፍፍፍፍ በየሱስ ስም ምንድነው የሰራሁት? ዶክተር ሰይፈ በሙያው ማንም እንከን የማያወጣለት ጎበዝ ነው። በተደጋጋሚ እያረፈደ እና እየቀረ ስላስቸገረ ቦርዱን ሰብስቤ ከስራው እንዲባረር ያደረግኩት ቀን ያሳየኝን ፊት ትርጉም የምረዳው አሁን ነው። ምክንያቱን እንኳን ሊነግረኝ የደከመው ነበር የሚመስለው። እሺ ብቻ ነበር ያለኝ። ከቦርድ አባላቱ አንዱ ምክንያቱን እንድሰማው ጠይቆኝ ነበር። «ተውት ምክንያቴን ለእናንተ እያስረዳሁ ህመሜን አላበዛም። ለእስከዛሬው ቆይታችን አመሰግናለሁ!» ያለው በሰአቱ ምን ያለ መስሎኝ ነው ከምንም ያልቆጠርኩት? እንዴት ግን አንዳቸው እንኳን ልጁን እያስታመመ ነው አይሉኝም? ይሄን ያህል ድንጋይ ልብ ያለኝ ነው የምመስላቸው? ይጠሉኛል ማለት ነው አይደል?
ማሰብ ይደክማል እንዴ? ማሰብ ደከመኝ:: ስልኬ መልዕክት መቀበሉን ነገረኝ። ከፈትኩት። የማላውቀው ቁጥር ነው።
“ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ አይነኬ የህይወት ክፍል አለው። ያን ሽሽት የሆነ ነገር ውስጥ ይደበቃል። ሌት ተቀን ህሙማንን ማገልገልሽ ለብዙዎች ታታሪነትሽን ይነግራቸዋል። ስራሽ መደበቂያሽ መሆኑን ግን አሳምረሽ ታውቂዋለሽ።”
ከሱ ውጪ ማንም አይሆንም። ቁጥሩን ደወልኩበት። ይሄ ደግሞ ሊያሳብደኝ ነው እንዴ ሀሳቡ?
“ምንድነው ከኔ የምትፈልገው? ምንድነው ግን ችግርህ?”
“ደህና እግዜአብሄር ይመስገን!! ምሳ እንኳን አይመቸኝም። እራት ቢሆንልኝ እመርጣለሁ።” አለኝ ዘና ብሎ።
ምን ልለው ነበር የደወልኩት? ቁጣዬን ምላሴ ላይ ምን ያልከሰክሰዋል?
“እራት ልጋብዝሽ?” አለኝ ዝምታዬን ተከትሎ። ምን እንደምመልስለት ግራ ገባኝ።
“ማሂ ፕሊስ?……… እኔ ደስ ብቻ ነው የሚለኝ። ዶክተር ማህደር እራት ተጋበዘችልኝ ብዬ ቀላል ሴት የሆንሽ አይመስለኝም።” የማስበውን እኔ ከስቤ ሳልጨርሰው ከሱ አፍ እሰማዋለሁ።
“የባለፈው ሬስቶራንት 12 ሰዓት ላይ ላግኝሽ! ውብ ቀን ዋዩ!!” ብሎኝ እንቢም እሺም ሳልለው ስልኩን ዘጋው።

⚫️ይቀጥላል⚫️

ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳችሁ Like👍👍 እያደረጋችሁ የኔ ምርጦች😘


ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍122