#ወንጀልና_ቅጣት
:
ክፍል-አንድ
✍
:
:
በ ሕይወት እምሻው
እትዬ ሌንሴ ፊት ነሱኝ።
ለወትሮው ከፊልድ ምናምን ስመለስ እንኳን ኬሻ ሙሉ ከሰል፣ ሶስት አራት ኪሎ ቲማቲም ወይ ሽንኩርት ወይ ደግሞ ጎመን ምናምን ይዤ መጥቼ የመኪናዬን ጲጵ ሲሰሙ ጠብ እርግፍ ብለው ያስተናግዱኝ ነበር። ቤት ያፈራውን ጭኮ፣ ቅንጬ ወይም ፍርፍር በፍጥነት አቅርበው በግድ ያስበሉኝ ነበር።
ዛሬ ግን በተወደደ ከሰል ከየትና የት ካለ ኩሊ ራሴ አውርጄ (እጄ ከሰል በከሰል ሆኗል) ሳሎናቸው ስገባ እዛ…ሁልጊዜ የሚቀመጡበት አሮጌ ፎቴ ላይ የሚወደውን ሰው መርዶ የሰማ ሰው መስለው ተጎልተዋል።
ሃሳብ ገብቷቸው አልሰሙኝ ይሆን?
ሁሌም ወፍራም ላስቲክ የሚለብሰውን ምንጣፋቸውን በጭቃ ጫማዬ እንዳላቆሽሽ እየተሳቀቅኩ፣ ከሰል በከሰል የሆነ እጄን እነዳንከረፈፍኩ አጠገባቸው ደርሼ ሰላም ልላቸው ብጠጋቸው እያዩኝ እንደማያዩ መስለው ፊት ነሱኝ።
ምን አጥፍቼ ነው?
– እንዴት ሰነበቱ እትዬ ሌንሴ ከማለቴ
– አረ ምንጣፌን! ምንጣፌን አታቆሽሽብኝ እንጂ…ለራሴ ሰራተኛም የለኝ… አሉኝና ደልዳላ ሰውነታቸውን እያሞናደሉ ወደ ጓዳ ገቡ።
አረ ፊት መንሳት!
መጥፎ ሰው አይደለሁም። ያው እንደሁሉም ሰው ስህተትና ጥቂት ደደብነት ባያጣኝም መጥፎ ሰው አይደለሁም። አንድ መጥፎ ነገር ያደረገ ሰው መጥፎ ሰው ነው? አይመስለኝም።
የፍቅረኛዬ እናት እትዬ ሌንሴ ለምን እንደተናደዱብኝ የጠረጠርኩት ባዶው ሳሎን ውስጥ ጥለውኝ ጓዳ በገቡ በደቂቃዎች ውስጥ ነው። ቤዛ የሰራሁትን ስህተት ነግራቸው ነው።
ወሬኛ።
እጆቼን እንዳንከረፈፍኩ መታጠቢያ ውሃ ፍለጋ ደጅ ወጣሁ።
የቤዛ ታላቅ እህት ምህረት ፊቷን ካመጣሁት ከሰል አጥቁራ ጠበቀችኝ።
– አረ ውሃ ፈልገሽ አስታጥቢኝ በናትሽ አልኳት ሰላምታ ለመስጠም ሳልሞክር። በአይኖቿ ሰማይ ድረስ አጉናኝ መሬት ስታፈርጠኝ ይታወቀኛል። (እሷም ሰምታለች ማለት ነው። )
– ውሃ የለችም…ቤትህ ታጠብ…ብላኝ በረንዳ ላይ ያስቀመጥኩትን ኬሻ ሙሉ ከሰል ልክ እንደሰው ገላምጣው ጥላኝ ወደ ቤት ገባች።
ይህችን ይወዳል ሚካኤል!
በሁለቱም ሁኔታ እየተበሳጨሁ ያመጣሁትን ከሰል ብድግ አድርገህ ለራስህ እናት ውሰድ ውሰድ እያለኝ ወደ መኪናዬ ስሄድ የቤዛ ትንሽ እህት እምነት ገጠመችኝ። እኔንና እጆቼን አመሳቅላ አይታ…
– ምነው ውሃ የለም እንዴ በቤቱ? አለችኝ (ይህችኛዋ ገና አልሰማችም ማለት ነው)
– ማዘርም ምህረትም ፊት ነሱኝ…ማን ያስታጥበኝ…አልኳት አይን አይኗን እያየሁ
– አውነታቸውን ነው ለነገሩ…እንዳንተ አይነቱ ቆሻሻ እንኳን በጆግ ውሃ በአባይም ቢታጠብ አይነፃ! አለችና መልስ እንኳን ሳትጠብቅ እየተመናቀረች ጥላኝ ሄደች። (ሰምታለች)
አሁን ነገሩ ፍንትው አለልኝ። የወሬ ሰንሰለቱ ተገለጠልኝ። ቤዛ እና ቤተሰቧ እንደማይለያይ መንጋ ናቸው። የሚያስቡት አንድ ላይ። የሚስቁት አንድ ላይ። የሚያኮርፉት አንድ ላይ። የሚወዱት አንድ ላይ። የሚጠሉት አንድ ላይ። ወሬ አይደባበቁ…ምስጢር አያውቁ…ብሽቆች።
መኪናዬ ውስጥ ገብቼ በአንዱ ቁራጭ ፎጣ የእጆቼን ከሰል ለማስለቀቅ ስሞክር ንዴቴ ጨመረ።
ለምን ነገረቻቸው?
ይቅር ብዬሃለሁ ምናምን ብላኝ ለምን ስለስህተቴ ለቤተሰቧ ነገረች? ስለግል ጉዳያችን ለቤተሰብ ቱስ ማለቱ…እኔን ከማስገመት በቀር ምንድነው ትርጉሙ? ቤት ቤት ከወንጀሌ የማይመጣጠን የምትቀጣኝ ቅጣት አንሶ ይወዱኝ በነበሩ ቤተሰቦቿ ዘንድ ቀልዬ እንድታይ ለማድረግ?
…ነገሩ ቆይቷል። ማለቴ አንድ አምስት ወር አልፎታል። አብረን መኖረ ሲቀረን ሳንጋባ የተጋባን ጥንዶች ሆነን ነበር። ቤተሰብ ያውቀኛል። ቤተሰብ ያውቃታል። ከሳምንቱ አብዛኛውን ቀን አብረን ውለን እናድራለን። ጉሮ ወሸባዬ እና አሸወይና እና የማዘጋጃ ቤት ፊርማ ሲቀር ተጋብተናል ሊባል ይችል ነበር። በዛው ሰሞን ከየት መጣ ሳልለው ቤዛ አድርጋ የማታውቀውን የ‹‹እንጋባ›› ንዝንዛዋን መጀመሪያ ለዘብ፣ በኋላ ክርር አድርጋ ጀመረች።
አይኗ ከቬሎ ሱቆች፣ ሃሳቧ ከሰርግ አልላቀቅ አለ። እኔ ደግሞ ላገባ (ት) አልፈለግኩም። ስለማልወዳት አይደለም። እወዳታለሁ። ላገባት የማልፈልገው እንደወደድኳት መቆየት ስለምፈልግ ነው።
ከአምስቱ የቅርብ ጓደኞቼ ሶስቱን ሚዜ ሆኜ ድሬያለሁ። ከተጋቡ ወዲህ በደስታቸው ፈንታ የጨመረው ቦርጭና ንጭንጫቸው ብቻ ነው። ጋኔን አይደለም ያገቡት። ያፈቀሯቸውን ሴቶች ነው ያገቡት። ግን አንድም ቀን ስለትዳር ወይ ስለሚስት በጎ ነገር ሲወጣቸው አላየሁም። አልሰማሁም።
ቅልጥ ያለ ፑል እየተጫወትን ተደውሎ ይጠራሉ።
…ዳይፐር እንዳትረሳ…ምጣዱ እንደገና ተበላሽቷል። …የውሃ ዛሬ መክፈል አለብህ….ባቢ ትኩሳት አለው…የእማማ ማህበር እኮ ዛሬ ነው…
ቶሎ ና።
ቶሎ ድረስ።
አሁኑኑ እንድትመጣ።
እንዳታረፍድ።
እንዳታመሽ። …
እንዲህ ያሉ ትእዛዞች በሚበዙበት የጭቆና አገዛዝ ወድቀዋል። እኔ ደግሞ ነፃነቴን አጥብቄ የምወድ ሰው ነኝ። ድንበር፣ መስመር፣ ሰአት እላፊ አልወድም። ትእዛዝ ይጎረብጠኛል። መሆን አለበት ያመኛል። እንዲህ አድርግ ይረብሸኛል።
ቤዛንም ነፃነቴንም እወዳለሁና የትዳርን እግረ-ሙቅ ‹ትንሽ እንቆይ›› ምናምን ብዬ በጨዋኛ እምቢ አልኳት።
አቤት አለዋወጥ! ተለዋወጠችብኝ። ለሕይወቷ የሰጋች እስስት እንዲደዚሀ አትለዋወጥም። ይባስ ብላ…
– እማዬ ወንድ ልጅ የሚፈልገውን ነገር ሁሉ ከትዳር በፊት ካገኘ አያገባሽም ብላኛለች ብላ ለሁለት ወር ተኩል የምወደውን፣ የምኖርለትን ገላዋን ከለከለችኝ።
አበድኩ። ማለቴ በጣም አበድኩ። የገዛ ገርልፍሬንዴ ጭኖች መሃ ለመግባት የትዳር የምስክር ወረቀት ስጠየቅ ጊዜ በጣም ተናደድኩ።
ደግሞ እኮ ልታሰቃየኝ አብራኝ ታድራለች። ልክ ዛሬ ራራችልኝ..ፈቀደችልኝ፣ ቅጣቴ ሊያበቃ ነው ምናምን ብዬ ሁለመናዬ እንደ ጅብራ ሲገተር እንደ ታናሸ ወንድም ግንባሬን ስማኝ ራሷን በመአት ትራሶች አጥራ ትተኛለች።
ከይሲ አይደለች?
ብላት- ብሰራት ሁለት ወር ተኩል ሙሉ ራሷን ነፈገችኝ። አስቡት፤ ወንድ ነኝ። ወጣት ነኝ። ከቆንጆ ሴት አጠገብ የተኛሁ ወጣት ወንድ ነኝ። የፍትወት ፍላጎት ብቻ ሳይሆን ትዝታ አለኝ።
ከይሲ ናት።
ቢሆንም አይኔ ሌላ አላማተረም። ልቤ ለሌላ አልነሆለለም። ቅጣቱ እንዲቀልልኝ፣ በምህረቷ እንድትጎበኘኝ ብሞት አድርጌ የማላውቀውን በፊልም እንደማያቸው ወንዶች አበባ ምናምን እየገዛሁ እሰጣት ጀመር። መብራት ሳይጠፋ ሻማ ምናምን ለኩሼ፣ ወይን ቀድቼ ላሳዝናት ሞከርኩ። እሷ ግን ፍንክች አላለችም።
ገላዋን እያዛጋሁ ሳምንታት አለፉ።
አንጎሌና ገላዬ ሌላ ማሰብ በማይችልበት በዚህ ከፍተኛ የወሲብ ድርቅ ጊዜ ነው የቢሯችን ኤች አር አፈር ይብላና ሄርሜላን የቀጠረው።
ኦ…ሄርሜላ!
ለድርጅቱ በገንዘብ ያዥነት የተቀጠረች ሳይሆን ለኔ በፈተናነት የመጣች ትመስል ነበር። የሆነች እንከን አልባ ነገር። ሹ…ል እና ትልልቅ ጡቶች። ሙትት ያለ አንጀት። በቀጭን ወገቧ እህህህ…እያለች በመከራ የምትጎትተው ትልቅ ቂጥ። ስስ ግን ሳሙኝ፣ ግመጡኝ የሚል ከንፈር። …
ሄርሜላ.....
💫ይቀጥላል💫
Like👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን
:
ክፍል-አንድ
✍
:
:
በ ሕይወት እምሻው
እትዬ ሌንሴ ፊት ነሱኝ።
ለወትሮው ከፊልድ ምናምን ስመለስ እንኳን ኬሻ ሙሉ ከሰል፣ ሶስት አራት ኪሎ ቲማቲም ወይ ሽንኩርት ወይ ደግሞ ጎመን ምናምን ይዤ መጥቼ የመኪናዬን ጲጵ ሲሰሙ ጠብ እርግፍ ብለው ያስተናግዱኝ ነበር። ቤት ያፈራውን ጭኮ፣ ቅንጬ ወይም ፍርፍር በፍጥነት አቅርበው በግድ ያስበሉኝ ነበር።
ዛሬ ግን በተወደደ ከሰል ከየትና የት ካለ ኩሊ ራሴ አውርጄ (እጄ ከሰል በከሰል ሆኗል) ሳሎናቸው ስገባ እዛ…ሁልጊዜ የሚቀመጡበት አሮጌ ፎቴ ላይ የሚወደውን ሰው መርዶ የሰማ ሰው መስለው ተጎልተዋል።
ሃሳብ ገብቷቸው አልሰሙኝ ይሆን?
ሁሌም ወፍራም ላስቲክ የሚለብሰውን ምንጣፋቸውን በጭቃ ጫማዬ እንዳላቆሽሽ እየተሳቀቅኩ፣ ከሰል በከሰል የሆነ እጄን እነዳንከረፈፍኩ አጠገባቸው ደርሼ ሰላም ልላቸው ብጠጋቸው እያዩኝ እንደማያዩ መስለው ፊት ነሱኝ።
ምን አጥፍቼ ነው?
– እንዴት ሰነበቱ እትዬ ሌንሴ ከማለቴ
– አረ ምንጣፌን! ምንጣፌን አታቆሽሽብኝ እንጂ…ለራሴ ሰራተኛም የለኝ… አሉኝና ደልዳላ ሰውነታቸውን እያሞናደሉ ወደ ጓዳ ገቡ።
አረ ፊት መንሳት!
መጥፎ ሰው አይደለሁም። ያው እንደሁሉም ሰው ስህተትና ጥቂት ደደብነት ባያጣኝም መጥፎ ሰው አይደለሁም። አንድ መጥፎ ነገር ያደረገ ሰው መጥፎ ሰው ነው? አይመስለኝም።
የፍቅረኛዬ እናት እትዬ ሌንሴ ለምን እንደተናደዱብኝ የጠረጠርኩት ባዶው ሳሎን ውስጥ ጥለውኝ ጓዳ በገቡ በደቂቃዎች ውስጥ ነው። ቤዛ የሰራሁትን ስህተት ነግራቸው ነው።
ወሬኛ።
እጆቼን እንዳንከረፈፍኩ መታጠቢያ ውሃ ፍለጋ ደጅ ወጣሁ።
የቤዛ ታላቅ እህት ምህረት ፊቷን ካመጣሁት ከሰል አጥቁራ ጠበቀችኝ።
– አረ ውሃ ፈልገሽ አስታጥቢኝ በናትሽ አልኳት ሰላምታ ለመስጠም ሳልሞክር። በአይኖቿ ሰማይ ድረስ አጉናኝ መሬት ስታፈርጠኝ ይታወቀኛል። (እሷም ሰምታለች ማለት ነው። )
– ውሃ የለችም…ቤትህ ታጠብ…ብላኝ በረንዳ ላይ ያስቀመጥኩትን ኬሻ ሙሉ ከሰል ልክ እንደሰው ገላምጣው ጥላኝ ወደ ቤት ገባች።
ይህችን ይወዳል ሚካኤል!
በሁለቱም ሁኔታ እየተበሳጨሁ ያመጣሁትን ከሰል ብድግ አድርገህ ለራስህ እናት ውሰድ ውሰድ እያለኝ ወደ መኪናዬ ስሄድ የቤዛ ትንሽ እህት እምነት ገጠመችኝ። እኔንና እጆቼን አመሳቅላ አይታ…
– ምነው ውሃ የለም እንዴ በቤቱ? አለችኝ (ይህችኛዋ ገና አልሰማችም ማለት ነው)
– ማዘርም ምህረትም ፊት ነሱኝ…ማን ያስታጥበኝ…አልኳት አይን አይኗን እያየሁ
– አውነታቸውን ነው ለነገሩ…እንዳንተ አይነቱ ቆሻሻ እንኳን በጆግ ውሃ በአባይም ቢታጠብ አይነፃ! አለችና መልስ እንኳን ሳትጠብቅ እየተመናቀረች ጥላኝ ሄደች። (ሰምታለች)
አሁን ነገሩ ፍንትው አለልኝ። የወሬ ሰንሰለቱ ተገለጠልኝ። ቤዛ እና ቤተሰቧ እንደማይለያይ መንጋ ናቸው። የሚያስቡት አንድ ላይ። የሚስቁት አንድ ላይ። የሚያኮርፉት አንድ ላይ። የሚወዱት አንድ ላይ። የሚጠሉት አንድ ላይ። ወሬ አይደባበቁ…ምስጢር አያውቁ…ብሽቆች።
መኪናዬ ውስጥ ገብቼ በአንዱ ቁራጭ ፎጣ የእጆቼን ከሰል ለማስለቀቅ ስሞክር ንዴቴ ጨመረ።
ለምን ነገረቻቸው?
ይቅር ብዬሃለሁ ምናምን ብላኝ ለምን ስለስህተቴ ለቤተሰቧ ነገረች? ስለግል ጉዳያችን ለቤተሰብ ቱስ ማለቱ…እኔን ከማስገመት በቀር ምንድነው ትርጉሙ? ቤት ቤት ከወንጀሌ የማይመጣጠን የምትቀጣኝ ቅጣት አንሶ ይወዱኝ በነበሩ ቤተሰቦቿ ዘንድ ቀልዬ እንድታይ ለማድረግ?
…ነገሩ ቆይቷል። ማለቴ አንድ አምስት ወር አልፎታል። አብረን መኖረ ሲቀረን ሳንጋባ የተጋባን ጥንዶች ሆነን ነበር። ቤተሰብ ያውቀኛል። ቤተሰብ ያውቃታል። ከሳምንቱ አብዛኛውን ቀን አብረን ውለን እናድራለን። ጉሮ ወሸባዬ እና አሸወይና እና የማዘጋጃ ቤት ፊርማ ሲቀር ተጋብተናል ሊባል ይችል ነበር። በዛው ሰሞን ከየት መጣ ሳልለው ቤዛ አድርጋ የማታውቀውን የ‹‹እንጋባ›› ንዝንዛዋን መጀመሪያ ለዘብ፣ በኋላ ክርር አድርጋ ጀመረች።
አይኗ ከቬሎ ሱቆች፣ ሃሳቧ ከሰርግ አልላቀቅ አለ። እኔ ደግሞ ላገባ (ት) አልፈለግኩም። ስለማልወዳት አይደለም። እወዳታለሁ። ላገባት የማልፈልገው እንደወደድኳት መቆየት ስለምፈልግ ነው።
ከአምስቱ የቅርብ ጓደኞቼ ሶስቱን ሚዜ ሆኜ ድሬያለሁ። ከተጋቡ ወዲህ በደስታቸው ፈንታ የጨመረው ቦርጭና ንጭንጫቸው ብቻ ነው። ጋኔን አይደለም ያገቡት። ያፈቀሯቸውን ሴቶች ነው ያገቡት። ግን አንድም ቀን ስለትዳር ወይ ስለሚስት በጎ ነገር ሲወጣቸው አላየሁም። አልሰማሁም።
ቅልጥ ያለ ፑል እየተጫወትን ተደውሎ ይጠራሉ።
…ዳይፐር እንዳትረሳ…ምጣዱ እንደገና ተበላሽቷል። …የውሃ ዛሬ መክፈል አለብህ….ባቢ ትኩሳት አለው…የእማማ ማህበር እኮ ዛሬ ነው…
ቶሎ ና።
ቶሎ ድረስ።
አሁኑኑ እንድትመጣ።
እንዳታረፍድ።
እንዳታመሽ። …
እንዲህ ያሉ ትእዛዞች በሚበዙበት የጭቆና አገዛዝ ወድቀዋል። እኔ ደግሞ ነፃነቴን አጥብቄ የምወድ ሰው ነኝ። ድንበር፣ መስመር፣ ሰአት እላፊ አልወድም። ትእዛዝ ይጎረብጠኛል። መሆን አለበት ያመኛል። እንዲህ አድርግ ይረብሸኛል።
ቤዛንም ነፃነቴንም እወዳለሁና የትዳርን እግረ-ሙቅ ‹ትንሽ እንቆይ›› ምናምን ብዬ በጨዋኛ እምቢ አልኳት።
አቤት አለዋወጥ! ተለዋወጠችብኝ። ለሕይወቷ የሰጋች እስስት እንዲደዚሀ አትለዋወጥም። ይባስ ብላ…
– እማዬ ወንድ ልጅ የሚፈልገውን ነገር ሁሉ ከትዳር በፊት ካገኘ አያገባሽም ብላኛለች ብላ ለሁለት ወር ተኩል የምወደውን፣ የምኖርለትን ገላዋን ከለከለችኝ።
አበድኩ። ማለቴ በጣም አበድኩ። የገዛ ገርልፍሬንዴ ጭኖች መሃ ለመግባት የትዳር የምስክር ወረቀት ስጠየቅ ጊዜ በጣም ተናደድኩ።
ደግሞ እኮ ልታሰቃየኝ አብራኝ ታድራለች። ልክ ዛሬ ራራችልኝ..ፈቀደችልኝ፣ ቅጣቴ ሊያበቃ ነው ምናምን ብዬ ሁለመናዬ እንደ ጅብራ ሲገተር እንደ ታናሸ ወንድም ግንባሬን ስማኝ ራሷን በመአት ትራሶች አጥራ ትተኛለች።
ከይሲ አይደለች?
ብላት- ብሰራት ሁለት ወር ተኩል ሙሉ ራሷን ነፈገችኝ። አስቡት፤ ወንድ ነኝ። ወጣት ነኝ። ከቆንጆ ሴት አጠገብ የተኛሁ ወጣት ወንድ ነኝ። የፍትወት ፍላጎት ብቻ ሳይሆን ትዝታ አለኝ።
ከይሲ ናት።
ቢሆንም አይኔ ሌላ አላማተረም። ልቤ ለሌላ አልነሆለለም። ቅጣቱ እንዲቀልልኝ፣ በምህረቷ እንድትጎበኘኝ ብሞት አድርጌ የማላውቀውን በፊልም እንደማያቸው ወንዶች አበባ ምናምን እየገዛሁ እሰጣት ጀመር። መብራት ሳይጠፋ ሻማ ምናምን ለኩሼ፣ ወይን ቀድቼ ላሳዝናት ሞከርኩ። እሷ ግን ፍንክች አላለችም።
ገላዋን እያዛጋሁ ሳምንታት አለፉ።
አንጎሌና ገላዬ ሌላ ማሰብ በማይችልበት በዚህ ከፍተኛ የወሲብ ድርቅ ጊዜ ነው የቢሯችን ኤች አር አፈር ይብላና ሄርሜላን የቀጠረው።
ኦ…ሄርሜላ!
ለድርጅቱ በገንዘብ ያዥነት የተቀጠረች ሳይሆን ለኔ በፈተናነት የመጣች ትመስል ነበር። የሆነች እንከን አልባ ነገር። ሹ…ል እና ትልልቅ ጡቶች። ሙትት ያለ አንጀት። በቀጭን ወገቧ እህህህ…እያለች በመከራ የምትጎትተው ትልቅ ቂጥ። ስስ ግን ሳሙኝ፣ ግመጡኝ የሚል ከንፈር። …
ሄርሜላ.....
💫ይቀጥላል💫
Like👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን
👍11
#ወንጀልና_ቅጣት
:
ክፍል-ሁለት
✍
:
:
በ ሕይወት እምሻዉ
...ፈተናዬን ሲያበዙት ፊልድ በሄድኩ ቁጥር ስልጠናው ላይ አበል ትክፈል ብለው አብረው ይልኩናል። ሃዋሳ ላይ ለትንሽ አመለጥኳት….መቀሌ ላይ ለጥቂት ሳትኳት፣ አርባምንጭ በመከራ አለፍኳት …ደሴ ግን…ደሴ ላይ ግን ብርዱና ውበቷ አሲረውብኝ ወደቅኩላት። ቀመስኳት። አጣጣምኳት። የተመኘሁትን ጡት እንደ መንፈቅ ልጅ መጠመጥኩ። የጓጓሁለትን ወገብ አቀፍኩ። የቋመጥኩለትን መቀመጫ ጨብጥኩ። ያለምኩትን ከንፈር ጎረስኩ።
ሲነጋ በአንሶላ ተጠቅልላ አይን አይኔን ስታየኝ ነቃሁ። ከባይተዋር ሰው ጋር ባይተዋር አልጋ ላይ ተኝቴ ሲነጋብኝ ፍንጣሪ የጥፋተኝነት ስሜት ስላልተሰማኝ ጥፋተኝነት ተሰማኝ። ትራሴን ተንተርሼ እንደተኛሁ ፣ እንዴት አደርሽ እንኳን ሳልላት-
– ስሚ ሄርሜላ…ትላንት…ስህተት ነው የሰራነው….እኔ እጮኛ አለኝ…አልኳት
– አራቴ ስህተት አለ? ሃሃ….አለችና ያን ከንፈሯን ይዛ ወደከንፈሬ ስትጠጋ ሸሸት ብዬ..
– የምሬን ነው…ስህተት ነው….እጮኛዬን እወዳታለሁ…አልኩ
በፍፁም ግዴለሽነት ከአልጋ ውስጥ ውስጥ መለመላዋን ወጥታ ፈት ለፊቴ ቆመች። ከእኔ በፊት እዚህ ቦታ ሺህ ጊዜ የቆመች፣ ሺህ ጊዜ የሌላን ሰው ገላ አቅፋ ያደረች ልምድ ያላት አሳሳች ትመስላለች።
– አንድ ነገር አንዴ ከሆነ ስህተት ከተደጋገመ ውሳኔ ነው የሚባለው….ለማንኛውም ይመችህ…ሰአት ሄዷል …ልታጠብ…ብላ ታላቅ ቂጧን እያገላበጠች ወደ መታጠቢያው ክፍል ሄደች…
ምንድነው ያለችው?
አዲሳባ ስመለስና ቤዛን ሳገኛት ፀፀት ይሰማኛል፣ የሰራሁት ሃጥያት ያሰቃየኛል ብዬ ጠብቄ ነበር። ያልተለወጠው ግትር ባህሪዋ ይሆን የኔ አይኑን በጨው ያጠበ ባለጌ ሰው መሆን ሽውም አላለኝ። የሄርሜላን ሴትነት ያገኘው ወንድነቴ ምሱን አገኘ መሰለኝ በትራስ ታጥሮ የሚተኛው የቤዛ ገላ አላጓጓው አለ። ማስፈራሪያና ቅጣቷ አልሰማው አለ።
ሄርሜላን በማስታገሻነት በወሰድኩ አንድ ሳምንት ካለፈ ይመስለኛል ቤዛ ባንዱ ምሽት እንደለመደችው ልታሰቃየኝ ስትሞክር ቀድሜያት ግንባሯን ሳምኩና ጀርባዬን ሰጥቼያት ተኛሁ። ደቂቃም ሳይቆይ በቀጫጭን ጣቶቿ ጀርባዬን ትዳብስ…እጆቿን ወደ ጉያዬ ትሰድ ጀመር።
ዝም አልኳት።
በግድ ወደ እሷ ገልብጣኝ-
– ሚኪዬ…አለችኝ በመኝታ ቤት ድምፅዋ…
– አቤት…አልኩ ቡዝ ያሉ ውብ አይኖቿን እያየሁ። ወደ ግራ ያዘነበለ አንገቷን፣ ጫፋቸው የከረረ ጡቶችዋን በስስ ካናቴራዋ ውስጥ እየታዘብኩ።
– አልናፈቅኩህም?…
– ናፍቀሽኛል….
– ምነው መጠየቅ እንኳን ተውክ ታዲያ…
– ጠይቄ ጠይቄ ሰለቸኛ!
ዘላ ተከመረችብኝ።
ቅጣቴ ባልጠበቅኩት ሁኔታ ተቋጭቶ የኔ ወደሆነው ቦታ እንድዘልቅ ተፈቀደልኝ።
ከዚያ ምሽት በኋላ እኔና ቤዛ የበፊቶቹ ሚኪና ቤዛ ሆንን። የአግባኝ ጥያቄዋ ከጭቅጭቅነት ወደ ልመና ዝቅ ብሎ አንጀት በሚበላ ሁኔታ የምታቀርበው ተማፅኖ ብቻ ሆነ። ከንግግር ይልቅ በሌላ መልኩ የምትገፋብኝ ረቂቅ አጀንዳ ሆነ። ሶፋ እንደመቀየር፣ የኩሽና ኮተት እንደማሟላት፣ ምጣድ እንደመግዛት፣ ሰፋ ያለ ቤት እንከራይ እንደማለት አይነት ረቂቅ አጀንዳ።
ግፊቷን ችዬ መደበኛ ሕይወት ወደመኖሬ ስመለስ አድብቶ የቆየው የአግባኝ ጥያቄዋ ተመልሶ መጣ። እጅ እጅ አለኝ።
– አንቺ ቆይ ለምን አትረጋጊም….እኔ ዝግጁ ሳልሆን ባገባሽ ጥሩ የሚሆን ይመስልሻል? አልኩ በአንዱ ቀን የጋለ ጭቅጭቅ ስንጀምር
– ምንድነው ምትጠብቀው? ቤትህ ተሟልቷል። ታውቀኛለሁ። አውቅሃለሁ። እንዋደዳለን…ምንድነው ምትጠብቀው…ከዚህ ወዲህ አዲስ ፀባይ አይኖረኝም…ለምን አታገባኝም…እጆቿን እያወናጨፈች….
– እንተዋወቃለን? እርግጠኛ ነሽ?
– ምን ማለት ነው ይሄ ደግሞ?
– ምንም ማለት አይደለም ግን ምን ያጣድፈናል?
– ምን ያጣድፈናል? ሶስት አመት በላይ አብረን ቆየን…ምን ይጎትተናል?
– ገና ነው..
– ገና አይደለም…ወይ አሁን ታገባኛለህ…ወይ እንለያያለን…በቃ…
– በቃ?!
– አዎ በቃ….
– ይሄው ነው ቤዛ?
– ይሄው ነው…እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም፡ ውሳኔው ያንተ ነው….
የመኝታ ቤት በሩን ያለርህራሄ ድርግም አድርጋ ዘግታው እዛው ዋለች።
እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም። እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም። እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም።
ሱቅ ሄጄ ስድሰት ቢራ ይዤ መጣሁና አንዱን ከፍቼ መጠጣት ጀመርኩ።
የመጨረሻ ጠርሙሴን ሳጋምስ ወደ ሳሎን ብቅ አለች።
አጠገቤ ቁጭ አለች። አንዴ እኔን አንዴ ባዶ የቢራ ጠርሙሶቹን አየችና
– ሚኪ….አለችኝ
– አቤት….
– አትወደኝም?….
– እወድሻለሁ…ግን ይሄን ማስፈራራት ማቆም አለብሽ…ትዳር አንደዚህ አይቆይም….
– የምን ማስፈራራት?
– ሴክስ የለም ምናምን….ብቸኛው የቅጣት መሳሪያሽ እሱ ይመስላል…ጥሩ አይደለም…..አልኩ ጠርሙሱን ጠረጴዛ ላይ አስቀምጬ እያየኋት…
– ጥሩ አይደለም ማለት…
– ማለት…የራበው ልጅ ምግብ ሰርቆም ቢሆን ይበላል…
ብድግ አለች።
– ምን አልክ አንተ!? ጮኸችብኝ።
– ምን አልኩ? ያልኩትን ነገር ለማሰብ ሞከርኩ። ምንድነው ያልኩት…
– የራበው ልጅ ምግብ ፍለጋ ይሰርቃል ማለት ምንድነው?
ወየው! ምንድነው ያልኩት? ምንድነው ያልኩት?
– ምንም ማለት አይደለም…አባባል ነው…
– አባባልማ አይደለም…በደንብ አስበህበት ነው የተናገርከው…
ወየው!
– ንገረኛ!
– ምን ልንገርሽ?
– ሰርቀሃል?
– እ?
– ሰርቀሃል ወይ?
ስድስቱ ቢራ ይሆን ግዴለሽነቴ ወይ ሁለቱም አዎ አልኳት። አልገርምም? አንዴ አምልጦኛል እና አዎ ሰርቄያለሁ አልኳት። ከግድግዳ መጋጨት ሲቀራት ሁሉን ነገር ሆነች። አለቀሰች። ጮኸች። በጥፊ ልትለኝ ሞከረች። ደጅ ወጣች። ተመልሳ ገባች። አለቀሰች። ጮኸች። ፀጉሯን ይዛ አቀርቅራ ብዙ የማይሰማኝ ነገር አለች።
አሳዘነችኝ። በጣም አሳዘነችኝ። ግን ደግሞ አስርባ ሄርሜላን እንድበላ ያደረገችኝ እሷ ናት በሚል ወልጋዳ ይሁን ትክክለኛ ሰበብ ፀፀት ሳይሰማኝ ቀረ። ገፍትራ ሄርሜላ ጉድጓድ የከተተችኝ እሷ ናት….ምናምን እያልኩ በመናገሬ ሳልፀፀት ዝም ብዬ የምትሆነውን አየሁ። ምናልባት የማላውቀው የልቤ ክፍል ለትዳር ዝግጁ ባለመሆኔ አላገባህም ብላ እንድትተወኝ…ሙሉ ነጻነቴን እንድታቀዳጀኝ ፈልጎ ይሆናል…ምናልባት….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
ክፍል-ሁለት
✍
:
:
በ ሕይወት እምሻዉ
...ፈተናዬን ሲያበዙት ፊልድ በሄድኩ ቁጥር ስልጠናው ላይ አበል ትክፈል ብለው አብረው ይልኩናል። ሃዋሳ ላይ ለትንሽ አመለጥኳት….መቀሌ ላይ ለጥቂት ሳትኳት፣ አርባምንጭ በመከራ አለፍኳት …ደሴ ግን…ደሴ ላይ ግን ብርዱና ውበቷ አሲረውብኝ ወደቅኩላት። ቀመስኳት። አጣጣምኳት። የተመኘሁትን ጡት እንደ መንፈቅ ልጅ መጠመጥኩ። የጓጓሁለትን ወገብ አቀፍኩ። የቋመጥኩለትን መቀመጫ ጨብጥኩ። ያለምኩትን ከንፈር ጎረስኩ።
ሲነጋ በአንሶላ ተጠቅልላ አይን አይኔን ስታየኝ ነቃሁ። ከባይተዋር ሰው ጋር ባይተዋር አልጋ ላይ ተኝቴ ሲነጋብኝ ፍንጣሪ የጥፋተኝነት ስሜት ስላልተሰማኝ ጥፋተኝነት ተሰማኝ። ትራሴን ተንተርሼ እንደተኛሁ ፣ እንዴት አደርሽ እንኳን ሳልላት-
– ስሚ ሄርሜላ…ትላንት…ስህተት ነው የሰራነው….እኔ እጮኛ አለኝ…አልኳት
– አራቴ ስህተት አለ? ሃሃ….አለችና ያን ከንፈሯን ይዛ ወደከንፈሬ ስትጠጋ ሸሸት ብዬ..
– የምሬን ነው…ስህተት ነው….እጮኛዬን እወዳታለሁ…አልኩ
በፍፁም ግዴለሽነት ከአልጋ ውስጥ ውስጥ መለመላዋን ወጥታ ፈት ለፊቴ ቆመች። ከእኔ በፊት እዚህ ቦታ ሺህ ጊዜ የቆመች፣ ሺህ ጊዜ የሌላን ሰው ገላ አቅፋ ያደረች ልምድ ያላት አሳሳች ትመስላለች።
– አንድ ነገር አንዴ ከሆነ ስህተት ከተደጋገመ ውሳኔ ነው የሚባለው….ለማንኛውም ይመችህ…ሰአት ሄዷል …ልታጠብ…ብላ ታላቅ ቂጧን እያገላበጠች ወደ መታጠቢያው ክፍል ሄደች…
ምንድነው ያለችው?
አዲሳባ ስመለስና ቤዛን ሳገኛት ፀፀት ይሰማኛል፣ የሰራሁት ሃጥያት ያሰቃየኛል ብዬ ጠብቄ ነበር። ያልተለወጠው ግትር ባህሪዋ ይሆን የኔ አይኑን በጨው ያጠበ ባለጌ ሰው መሆን ሽውም አላለኝ። የሄርሜላን ሴትነት ያገኘው ወንድነቴ ምሱን አገኘ መሰለኝ በትራስ ታጥሮ የሚተኛው የቤዛ ገላ አላጓጓው አለ። ማስፈራሪያና ቅጣቷ አልሰማው አለ።
ሄርሜላን በማስታገሻነት በወሰድኩ አንድ ሳምንት ካለፈ ይመስለኛል ቤዛ ባንዱ ምሽት እንደለመደችው ልታሰቃየኝ ስትሞክር ቀድሜያት ግንባሯን ሳምኩና ጀርባዬን ሰጥቼያት ተኛሁ። ደቂቃም ሳይቆይ በቀጫጭን ጣቶቿ ጀርባዬን ትዳብስ…እጆቿን ወደ ጉያዬ ትሰድ ጀመር።
ዝም አልኳት።
በግድ ወደ እሷ ገልብጣኝ-
– ሚኪዬ…አለችኝ በመኝታ ቤት ድምፅዋ…
– አቤት…አልኩ ቡዝ ያሉ ውብ አይኖቿን እያየሁ። ወደ ግራ ያዘነበለ አንገቷን፣ ጫፋቸው የከረረ ጡቶችዋን በስስ ካናቴራዋ ውስጥ እየታዘብኩ።
– አልናፈቅኩህም?…
– ናፍቀሽኛል….
– ምነው መጠየቅ እንኳን ተውክ ታዲያ…
– ጠይቄ ጠይቄ ሰለቸኛ!
ዘላ ተከመረችብኝ።
ቅጣቴ ባልጠበቅኩት ሁኔታ ተቋጭቶ የኔ ወደሆነው ቦታ እንድዘልቅ ተፈቀደልኝ።
ከዚያ ምሽት በኋላ እኔና ቤዛ የበፊቶቹ ሚኪና ቤዛ ሆንን። የአግባኝ ጥያቄዋ ከጭቅጭቅነት ወደ ልመና ዝቅ ብሎ አንጀት በሚበላ ሁኔታ የምታቀርበው ተማፅኖ ብቻ ሆነ። ከንግግር ይልቅ በሌላ መልኩ የምትገፋብኝ ረቂቅ አጀንዳ ሆነ። ሶፋ እንደመቀየር፣ የኩሽና ኮተት እንደማሟላት፣ ምጣድ እንደመግዛት፣ ሰፋ ያለ ቤት እንከራይ እንደማለት አይነት ረቂቅ አጀንዳ።
ግፊቷን ችዬ መደበኛ ሕይወት ወደመኖሬ ስመለስ አድብቶ የቆየው የአግባኝ ጥያቄዋ ተመልሶ መጣ። እጅ እጅ አለኝ።
– አንቺ ቆይ ለምን አትረጋጊም….እኔ ዝግጁ ሳልሆን ባገባሽ ጥሩ የሚሆን ይመስልሻል? አልኩ በአንዱ ቀን የጋለ ጭቅጭቅ ስንጀምር
– ምንድነው ምትጠብቀው? ቤትህ ተሟልቷል። ታውቀኛለሁ። አውቅሃለሁ። እንዋደዳለን…ምንድነው ምትጠብቀው…ከዚህ ወዲህ አዲስ ፀባይ አይኖረኝም…ለምን አታገባኝም…እጆቿን እያወናጨፈች….
– እንተዋወቃለን? እርግጠኛ ነሽ?
– ምን ማለት ነው ይሄ ደግሞ?
– ምንም ማለት አይደለም ግን ምን ያጣድፈናል?
– ምን ያጣድፈናል? ሶስት አመት በላይ አብረን ቆየን…ምን ይጎትተናል?
– ገና ነው..
– ገና አይደለም…ወይ አሁን ታገባኛለህ…ወይ እንለያያለን…በቃ…
– በቃ?!
– አዎ በቃ….
– ይሄው ነው ቤዛ?
– ይሄው ነው…እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም፡ ውሳኔው ያንተ ነው….
የመኝታ ቤት በሩን ያለርህራሄ ድርግም አድርጋ ዘግታው እዛው ዋለች።
እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም። እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም። እስክትወስን ሴክስ የሚባል ነገር የለም።
ሱቅ ሄጄ ስድሰት ቢራ ይዤ መጣሁና አንዱን ከፍቼ መጠጣት ጀመርኩ።
የመጨረሻ ጠርሙሴን ሳጋምስ ወደ ሳሎን ብቅ አለች።
አጠገቤ ቁጭ አለች። አንዴ እኔን አንዴ ባዶ የቢራ ጠርሙሶቹን አየችና
– ሚኪ….አለችኝ
– አቤት….
– አትወደኝም?….
– እወድሻለሁ…ግን ይሄን ማስፈራራት ማቆም አለብሽ…ትዳር አንደዚህ አይቆይም….
– የምን ማስፈራራት?
– ሴክስ የለም ምናምን….ብቸኛው የቅጣት መሳሪያሽ እሱ ይመስላል…ጥሩ አይደለም…..አልኩ ጠርሙሱን ጠረጴዛ ላይ አስቀምጬ እያየኋት…
– ጥሩ አይደለም ማለት…
– ማለት…የራበው ልጅ ምግብ ሰርቆም ቢሆን ይበላል…
ብድግ አለች።
– ምን አልክ አንተ!? ጮኸችብኝ።
– ምን አልኩ? ያልኩትን ነገር ለማሰብ ሞከርኩ። ምንድነው ያልኩት…
– የራበው ልጅ ምግብ ፍለጋ ይሰርቃል ማለት ምንድነው?
ወየው! ምንድነው ያልኩት? ምንድነው ያልኩት?
– ምንም ማለት አይደለም…አባባል ነው…
– አባባልማ አይደለም…በደንብ አስበህበት ነው የተናገርከው…
ወየው!
– ንገረኛ!
– ምን ልንገርሽ?
– ሰርቀሃል?
– እ?
– ሰርቀሃል ወይ?
ስድስቱ ቢራ ይሆን ግዴለሽነቴ ወይ ሁለቱም አዎ አልኳት። አልገርምም? አንዴ አምልጦኛል እና አዎ ሰርቄያለሁ አልኳት። ከግድግዳ መጋጨት ሲቀራት ሁሉን ነገር ሆነች። አለቀሰች። ጮኸች። በጥፊ ልትለኝ ሞከረች። ደጅ ወጣች። ተመልሳ ገባች። አለቀሰች። ጮኸች። ፀጉሯን ይዛ አቀርቅራ ብዙ የማይሰማኝ ነገር አለች።
አሳዘነችኝ። በጣም አሳዘነችኝ። ግን ደግሞ አስርባ ሄርሜላን እንድበላ ያደረገችኝ እሷ ናት በሚል ወልጋዳ ይሁን ትክክለኛ ሰበብ ፀፀት ሳይሰማኝ ቀረ። ገፍትራ ሄርሜላ ጉድጓድ የከተተችኝ እሷ ናት….ምናምን እያልኩ በመናገሬ ሳልፀፀት ዝም ብዬ የምትሆነውን አየሁ። ምናልባት የማላውቀው የልቤ ክፍል ለትዳር ዝግጁ ባለመሆኔ አላገባህም ብላ እንድትተወኝ…ሙሉ ነጻነቴን እንድታቀዳጀኝ ፈልጎ ይሆናል…ምናልባት….
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍10
#ወንጀልና_ቅጣት #የመጨረሻ_ክፍል
:
ክፍል-ሶስት
✍
:
:
በ ሕይወት እምሻዉ
...ሃጥያቴን በብቅል ግፊት ከተናዘዝኩ በኋላ መቼም ሰው አታደርገኝም…የኔ እና የእሷ ነገር አለቀ ደቀቀ ብዬ…ሂሳቤን አገኛለሁ ብዬ ስጠብቅ ሲሻት ተደብራ ከመጋገር፣ ሲሻት ከሰላምታ ያላለፈ ነገር ባለመናገር ከመቅጣት በቀር ትታኝ አልሄደችም።
እንደ ድሮው ቤቴ ትመጣለች፣ ስደውል ታነሳለች፣ እንገናኝ ስላት ታገኘኛለች። አብራኝ መተኛት ሲቀራት አብራኝ ትሆናለች። ሰብሬያት እንዳልሰበርኳት፣ አኩርፋኝ እንዳላኮረፈችኝ ትሆናለች። ዝም ስትለኝ ሰአቱ ቀን ይሆንብኛል። ቀኑ ሳምንት….ቅጣቴ ይሄ ነው? የሃጥያቴ ክፍያ በዝምታ መንገብገብ ነው?
ሶስት ቀን በሶስት አመታት ፍጥነት እየተጎተተ ካለፈ በኋላ ቁርጤን ልወቅ ብዬ ወሰንኩ። ቃተኛ ቁጭ ብለን ጥብስ ፍርፍራችንን በተለመደው ዝምታ ስንበላ
– ቤዚ…አልኳት
– እ….
መስረቄን ካወቀች ወዲህ ወዬዎቿ…በ እ…ተተክተዋል። ምንድነው እ ብሎ ነገር? ላናግርህ አልፈልግም ስለዚህ ከአንዲት ፊደል በቀር አይገባህም ነው?
– ይቅር ብለሽኛል? አልኳት ጥብስ ፍርፍሩን መብላትም ማየትም አቁሜ እያየኋት
– እ?
ኡፋ! …..የምን እ ነው?
– ይቅርታ አድርገሽልኛል ወይ….
– እዚህ ሰው ፊት ስለሱ ማውራት አልፈልግም…ቤት ስንሄድ እናወራለን….አለችኝ …ለአስተናጋጁ ሲሆን ከብርሃን የተሰራ የሚመስል ቀይ ዳማ ፊቷ ለኔ ሲሆን ባንዴ የሚዳምንላት እንዴት ነው?
ዝም ብያት እስክንጨርስ ጠበቅኩ።
ቤት ገባን። መልሼ ጠየቅኳት።
– አላውቅም…እያሰብኩበት ነው….አለችኝና ወደ መኝታ ቤት ሄደች።
ጓደኖቼን አማከርኩ። ይቅር ባትልህ አብራህ አትቆይም..ያደረግከው ነገር እኮ ከባድ ነው ትንሽ ታገስ…እሷ ሆና ነው እንጂ ሌላ ሴት ብትሆን ይሄኔ ቆርጣልህ ነበር…ምናምን ሲሉኝ የዝምታ ቅጣቴን በፀጋ ለመቀበል ወስኜ ቆየሁ።
ትንሽ ጊዜ ካለፈ በኋላ በአንዱ ቀነ ከመሬት ተነስታ ላንጋኖ እንሂድ ምናምን ብላ ወጠረችኝ።
– ለምን አልኳት
– እኔ ስለፈለግኩ አለችኝ። ፊቷን ሳየው ግን ‹‹ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛህ እና የፈለግኩትን ነገር ማድረግ ስላለብህ›› ተብሎ የተፃፈ መሰለኝ። እጄ ላይ ብዙ ብር አልነበረምና
– ደሞዝ ስቀበል…ከአስር ቀን በኋላ ብንሄድስ? አልኳት በሚለማመጥ ድምፅ…
– እኔ አሁን ነው መሄድ የፈለግኩት…ካልፈለግህ አልፈልግም በል….ብስጭትጭት አደረጋት።
ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛሁ ፣ ከጓደኛዬ ብር ተበደርኩና ሄድን።
ላንጋኖ ስንደርስ አይቼ የማላውቀውን ክር ሊሆን ትንሽ የቀረው ጡትና ቂጥ በአግባቡ የማይይዘ ‹‹የዋና ልብስ›› ለብሳ ልክ ብቻዋን እንደመጣች…ልክ ወንድ ልታጠመድ ታጥባ ተቀሽራ እንደወጣች ሴት ቢቹ ላይ ስትንቧችበት ዝም ብዬ አየኋት።
ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛሁ ብጉራቸውን እያፈረጡ ተጠግተዋት ሰልክ ቁጥር እየጠየቋት እንደሆነ የሚያስታውቁ ወንዶች ሲያንዣብቡባት፣ ሲያወሯት፣ በሚጢጢ ጨርቅ የተሸፈነ ምንተእፍረትዋን በአይናቸው ሲያወልቁ እያየሁ ዝም አልኳት።
ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛሁ ማታ ክፍላችን ገብተን ለማንም ኤግዚቢሽን ያቀረበችውን ገላዋን ለመንካት እንኳን ሰትከለክለኝ…እንደ እሾህ ስትሸሸኝ….አትንካኝ ሬዲ አይደለሁም ብላ ፍቅርን ስትነፍገኝ ዝም አልኳት።
አዲሳባ ተመልሰን የማልወደው ጫጫታም ካፌ እየወሰደች ለሰአታት አርፍዳ ስትጎልተኝ፣ አምስት ደቂቃ ዘግይቼ ቤት ከገባሁ አንበሳ ሆና ስትቆጣኝ፣ ከጓደኞቼ እንድቆራረጥ አትሄድም ብላ ስታስቀረኝ፣ የዘመዶቿን ሰርግ ይዛኝ ሄዳ ብቻዬን ትታኝ ስትረሳኝ፣ ሃጥያቴን ነግራቸው የናቁኝ ሴት ጓደኞቿን በሙሉ አምጥታ (አራት ናቸው) የሁለት መቶ ሃምሳ ብር ክትፎ ስታስጋብዘኝ…ከሌላ ሴት ተኝታቸለሁ እና ቅጣቴን ልቀበል…ሂሳቤን ላግኝ ብዬ ዝም አልኳት።
ይባስ ብላ አንዷ ቀለብላባ ጓደኛዋ በንቀትም በሴሰኝነትም ተነድታ ስልክም እየደወለች፣ ቤቴም ‹‹ቤዛ የለችም›› ብላ የሌለችበተትን ሰአት መርጥ እየመጣች እንድተኛት ስትጋብዘኝ…ከአንዷ ጋር ከማገጥክ ከእኛስ ጋር ብትማግጥ በሚል ሁኔታ ስትቀበጠበጥብኝ ጥፋቱ የኔ ነው ብዬ ዝም አልኳት።
ከሳምንታት በኋላ ግን እጅ እጅ እያለኝ መጣ። እኔን አስቀንታ ለመመለስ የምትለፋው፣ ላገኘችው ሰው ሁሉ ሃጥያቴን ነግራ ስሜን የምታጠፋው፣ በውሃ አረረ ፊቴን ፊት የምትነሳው፣ በሁሉም ነገር ስሜቴን የምታሸማቅቀው ነገር ከፍቅሯ እየበለጠ ነገሩ እጅ እጅ እያለኝ መጣ።
ጭራሽ አሁን ደግሞ ሃገር ውስጥ ስለሰራሁት ስህተት አልሰሙም ብዬ የተማመንኩባቸው እንደዛ የሚወዱኝ…እንደልጅ የሚንከባከቡኝ ቤተሰቦቿ ጋር ሄዳ ማውራቷ፣ ልታዋርደኝ መጨከኗ…በእኔና በእሷ ጉዳይ ማስገባቷ ልቤን አደነደነው። ልጠይቃት ይገባል። ይቅር ብለሽኛል ወይስ ቅጣቴ የእድሜ ልክ ነው? አፉ ብለሽኛል ወይስ አንቺ ካለሽበት ሕይወቴ እንዲህ ሊሆን ነው? ብዬ ልጠይቃት ይገባል።
እትዬ ሌንሴና እህቶቿ እንዲያ ባገባጠሩኝ እለት ማታ ቤት ቁጭ ብለን ወይን ስንጠጣ (ላወራት ስጀምር ነው አንዱን ጠርሙስ ጨርሳ ወደ ሁለተኛው መግባቷን ያየሁት)
– ቤዚ …አልኳት
– እ…
(እ…ን አሁንማ ለምጄዋለሁ)
– መቼ ነው እንደ ድሮው የምትሆኚልኝ? ቅጣቴ አልበዛም? አልኳት
– ያደረግከውን ነገር ረሳኸው…? ከሌላ ሴት ጋር እኮ ነው ሴክስ ያደረግከው…ሴ….ክ….ስ….
ወይኑም ነገሩም እንዳሰከራት ገባኝ።
-አውቃለሁ…አጠፋሁ…አይበቃኝም ቅጣቱ…እንዴት እንደዚህ እንቀጥላለን….ብንቀጥልስ…እስከመቼ ድሮ ለሰራሁት ጥፋት እድሜዬን ሙሉ እከፍላለሁ…
– ወር የማይሞላ ጊዜ ነው እድሜዬን ሙሉ የምትለው..
– አይደለም…
– ታዲያ…
– ማለቴ…ብንጋባ እንኳን አንድ ነገር ባጠፋሁ ቁጥር አንተ እኮ…እያልሽኝ እስከመቼ እንኖራለን…
– ሃሃ…..አሁን ነው መጋባት ያማረህ….? ደ…ፋ…ር….
ወሬያችን እንኳን እንዳሁኑ በአልኮል ፈረስ ተሳፍራ በደህናውም ጊዜ ትርጉም ያለው ነገር ሊወጣው እንደማይችል ተረዳሁና ዝም አልኳት።
– ምን ይ…ዘ…ጋ…ሃ…ል? አለች ፊደል እንደሚቆጥር ሰው ቃላቶቹን እየጎተተች…
– ጥቅም የለውም ብዬ ነው…
– ም…ኑ..
– እንዲህ ሆነሸ ማውራቱ….
– እና..ውራ…ማውራት አይደል የፈለግከው…እናውራ…
– ግዴለም ነገ ይደርሰል…
– አይ…ሆ…ን…ም አሁን እናውራ…
– ቤዚ…ይቅር
– አይ…ቀርም…እናውራ…እናወ…..ራ….
እንደለቅሶ ይሰራት ጀመር። ቤዚዬ….
– እሺ አልኳት እንዳታለቅስ…
– እሺ…ልጅቷ…እንዴት ነበረች…ጎበዝ ናት…..?
– ማ? አልኩኝ ደንገጥ ብዬ..
– እናውራ አላልክም…እናውራ….ያቺ አብረሃት የተኛሃት ልጅ…ጎበዝ ናት….ማለት…ከኔ ትበልጣለች?
ዝም አልኳት።
– ንገረኛ! እንዴት ነበረች…ትበልጠኛለች…..? ለቅሶ ጀመረች።
አቀፍኳት።
– ንገረኝ…..በለጠችኝ…ደስ አለችህ…ጎበዝ….
– ተይ ተይ በቃ…ቤዚዬ…ይቅርታ…በቃ…ይቅርታ አታልቅሺ አልኩና አጥብቄ አቅፌ ፀጉሯ ላይ…አይኖችዋን አፈራርቄ ሳምኳቸው።
– አትሳመኝ….ብላ ተፈናጥራ ተነሳች።
– እ?
– አትሳመኝ….እሷን በሳምክበት አፍ አትሳመኝ….ሚ..ኪ….ከሁሉ ሚያሳዝነኝ ምን እንደሆን ታውቃለህ…..አለችኝ ተመልሳ እየተቀመጠች።
ዝም አልኩ።
ቀጠለች-
– እወድሃለሁ…ማለቴ…ካላንተ ወንድ አልፈልግም…ጓደኞቼም ቤተሰቦቼም ቢመክሩኝም ባንተ መጨከን አቃተኝ…ሳምሪ ወንድ ልጅ አንዴ ከተልከሰከሰ ሁሌም ይልከሰከሳል…ይቅር ካልሽው እንደ ፈቃድ ነው ሚወስደው…ይቅርብሽ ብላኝ ነበር…ይሄን ታውቃለህ? እህቶቼ ለአይን ጠልተውሃል…እማዬማ ቤቴ አይምጣ ብላለች…እኔ ግን እወድሃለሁ…ልቤን ቢያመኝም…እወድሃለሁ…
– እነሱን ተያቸወ…አንቺ ከወደድሽኝ የኔ ጉዳይ ካንቺ ነው….አልኩ ፈጠን ብዬ…
– አይደለማ…..እወድሃለሁ ግን
:
ክፍል-ሶስት
✍
:
:
በ ሕይወት እምሻዉ
...ሃጥያቴን በብቅል ግፊት ከተናዘዝኩ በኋላ መቼም ሰው አታደርገኝም…የኔ እና የእሷ ነገር አለቀ ደቀቀ ብዬ…ሂሳቤን አገኛለሁ ብዬ ስጠብቅ ሲሻት ተደብራ ከመጋገር፣ ሲሻት ከሰላምታ ያላለፈ ነገር ባለመናገር ከመቅጣት በቀር ትታኝ አልሄደችም።
እንደ ድሮው ቤቴ ትመጣለች፣ ስደውል ታነሳለች፣ እንገናኝ ስላት ታገኘኛለች። አብራኝ መተኛት ሲቀራት አብራኝ ትሆናለች። ሰብሬያት እንዳልሰበርኳት፣ አኩርፋኝ እንዳላኮረፈችኝ ትሆናለች። ዝም ስትለኝ ሰአቱ ቀን ይሆንብኛል። ቀኑ ሳምንት….ቅጣቴ ይሄ ነው? የሃጥያቴ ክፍያ በዝምታ መንገብገብ ነው?
ሶስት ቀን በሶስት አመታት ፍጥነት እየተጎተተ ካለፈ በኋላ ቁርጤን ልወቅ ብዬ ወሰንኩ። ቃተኛ ቁጭ ብለን ጥብስ ፍርፍራችንን በተለመደው ዝምታ ስንበላ
– ቤዚ…አልኳት
– እ….
መስረቄን ካወቀች ወዲህ ወዬዎቿ…በ እ…ተተክተዋል። ምንድነው እ ብሎ ነገር? ላናግርህ አልፈልግም ስለዚህ ከአንዲት ፊደል በቀር አይገባህም ነው?
– ይቅር ብለሽኛል? አልኳት ጥብስ ፍርፍሩን መብላትም ማየትም አቁሜ እያየኋት
– እ?
ኡፋ! …..የምን እ ነው?
– ይቅርታ አድርገሽልኛል ወይ….
– እዚህ ሰው ፊት ስለሱ ማውራት አልፈልግም…ቤት ስንሄድ እናወራለን….አለችኝ …ለአስተናጋጁ ሲሆን ከብርሃን የተሰራ የሚመስል ቀይ ዳማ ፊቷ ለኔ ሲሆን ባንዴ የሚዳምንላት እንዴት ነው?
ዝም ብያት እስክንጨርስ ጠበቅኩ።
ቤት ገባን። መልሼ ጠየቅኳት።
– አላውቅም…እያሰብኩበት ነው….አለችኝና ወደ መኝታ ቤት ሄደች።
ጓደኖቼን አማከርኩ። ይቅር ባትልህ አብራህ አትቆይም..ያደረግከው ነገር እኮ ከባድ ነው ትንሽ ታገስ…እሷ ሆና ነው እንጂ ሌላ ሴት ብትሆን ይሄኔ ቆርጣልህ ነበር…ምናምን ሲሉኝ የዝምታ ቅጣቴን በፀጋ ለመቀበል ወስኜ ቆየሁ።
ትንሽ ጊዜ ካለፈ በኋላ በአንዱ ቀነ ከመሬት ተነስታ ላንጋኖ እንሂድ ምናምን ብላ ወጠረችኝ።
– ለምን አልኳት
– እኔ ስለፈለግኩ አለችኝ። ፊቷን ሳየው ግን ‹‹ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛህ እና የፈለግኩትን ነገር ማድረግ ስላለብህ›› ተብሎ የተፃፈ መሰለኝ። እጄ ላይ ብዙ ብር አልነበረምና
– ደሞዝ ስቀበል…ከአስር ቀን በኋላ ብንሄድስ? አልኳት በሚለማመጥ ድምፅ…
– እኔ አሁን ነው መሄድ የፈለግኩት…ካልፈለግህ አልፈልግም በል….ብስጭትጭት አደረጋት።
ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛሁ ፣ ከጓደኛዬ ብር ተበደርኩና ሄድን።
ላንጋኖ ስንደርስ አይቼ የማላውቀውን ክር ሊሆን ትንሽ የቀረው ጡትና ቂጥ በአግባቡ የማይይዘ ‹‹የዋና ልብስ›› ለብሳ ልክ ብቻዋን እንደመጣች…ልክ ወንድ ልታጠመድ ታጥባ ተቀሽራ እንደወጣች ሴት ቢቹ ላይ ስትንቧችበት ዝም ብዬ አየኋት።
ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛሁ ብጉራቸውን እያፈረጡ ተጠግተዋት ሰልክ ቁጥር እየጠየቋት እንደሆነ የሚያስታውቁ ወንዶች ሲያንዣብቡባት፣ ሲያወሯት፣ በሚጢጢ ጨርቅ የተሸፈነ ምንተእፍረትዋን በአይናቸው ሲያወልቁ እያየሁ ዝም አልኳት።
ከሌላ ሴት ጋር ስለተኛሁ ማታ ክፍላችን ገብተን ለማንም ኤግዚቢሽን ያቀረበችውን ገላዋን ለመንካት እንኳን ሰትከለክለኝ…እንደ እሾህ ስትሸሸኝ….አትንካኝ ሬዲ አይደለሁም ብላ ፍቅርን ስትነፍገኝ ዝም አልኳት።
አዲሳባ ተመልሰን የማልወደው ጫጫታም ካፌ እየወሰደች ለሰአታት አርፍዳ ስትጎልተኝ፣ አምስት ደቂቃ ዘግይቼ ቤት ከገባሁ አንበሳ ሆና ስትቆጣኝ፣ ከጓደኞቼ እንድቆራረጥ አትሄድም ብላ ስታስቀረኝ፣ የዘመዶቿን ሰርግ ይዛኝ ሄዳ ብቻዬን ትታኝ ስትረሳኝ፣ ሃጥያቴን ነግራቸው የናቁኝ ሴት ጓደኞቿን በሙሉ አምጥታ (አራት ናቸው) የሁለት መቶ ሃምሳ ብር ክትፎ ስታስጋብዘኝ…ከሌላ ሴት ተኝታቸለሁ እና ቅጣቴን ልቀበል…ሂሳቤን ላግኝ ብዬ ዝም አልኳት።
ይባስ ብላ አንዷ ቀለብላባ ጓደኛዋ በንቀትም በሴሰኝነትም ተነድታ ስልክም እየደወለች፣ ቤቴም ‹‹ቤዛ የለችም›› ብላ የሌለችበተትን ሰአት መርጥ እየመጣች እንድተኛት ስትጋብዘኝ…ከአንዷ ጋር ከማገጥክ ከእኛስ ጋር ብትማግጥ በሚል ሁኔታ ስትቀበጠበጥብኝ ጥፋቱ የኔ ነው ብዬ ዝም አልኳት።
ከሳምንታት በኋላ ግን እጅ እጅ እያለኝ መጣ። እኔን አስቀንታ ለመመለስ የምትለፋው፣ ላገኘችው ሰው ሁሉ ሃጥያቴን ነግራ ስሜን የምታጠፋው፣ በውሃ አረረ ፊቴን ፊት የምትነሳው፣ በሁሉም ነገር ስሜቴን የምታሸማቅቀው ነገር ከፍቅሯ እየበለጠ ነገሩ እጅ እጅ እያለኝ መጣ።
ጭራሽ አሁን ደግሞ ሃገር ውስጥ ስለሰራሁት ስህተት አልሰሙም ብዬ የተማመንኩባቸው እንደዛ የሚወዱኝ…እንደልጅ የሚንከባከቡኝ ቤተሰቦቿ ጋር ሄዳ ማውራቷ፣ ልታዋርደኝ መጨከኗ…በእኔና በእሷ ጉዳይ ማስገባቷ ልቤን አደነደነው። ልጠይቃት ይገባል። ይቅር ብለሽኛል ወይስ ቅጣቴ የእድሜ ልክ ነው? አፉ ብለሽኛል ወይስ አንቺ ካለሽበት ሕይወቴ እንዲህ ሊሆን ነው? ብዬ ልጠይቃት ይገባል።
እትዬ ሌንሴና እህቶቿ እንዲያ ባገባጠሩኝ እለት ማታ ቤት ቁጭ ብለን ወይን ስንጠጣ (ላወራት ስጀምር ነው አንዱን ጠርሙስ ጨርሳ ወደ ሁለተኛው መግባቷን ያየሁት)
– ቤዚ …አልኳት
– እ…
(እ…ን አሁንማ ለምጄዋለሁ)
– መቼ ነው እንደ ድሮው የምትሆኚልኝ? ቅጣቴ አልበዛም? አልኳት
– ያደረግከውን ነገር ረሳኸው…? ከሌላ ሴት ጋር እኮ ነው ሴክስ ያደረግከው…ሴ….ክ….ስ….
ወይኑም ነገሩም እንዳሰከራት ገባኝ።
-አውቃለሁ…አጠፋሁ…አይበቃኝም ቅጣቱ…እንዴት እንደዚህ እንቀጥላለን….ብንቀጥልስ…እስከመቼ ድሮ ለሰራሁት ጥፋት እድሜዬን ሙሉ እከፍላለሁ…
– ወር የማይሞላ ጊዜ ነው እድሜዬን ሙሉ የምትለው..
– አይደለም…
– ታዲያ…
– ማለቴ…ብንጋባ እንኳን አንድ ነገር ባጠፋሁ ቁጥር አንተ እኮ…እያልሽኝ እስከመቼ እንኖራለን…
– ሃሃ…..አሁን ነው መጋባት ያማረህ….? ደ…ፋ…ር….
ወሬያችን እንኳን እንዳሁኑ በአልኮል ፈረስ ተሳፍራ በደህናውም ጊዜ ትርጉም ያለው ነገር ሊወጣው እንደማይችል ተረዳሁና ዝም አልኳት።
– ምን ይ…ዘ…ጋ…ሃ…ል? አለች ፊደል እንደሚቆጥር ሰው ቃላቶቹን እየጎተተች…
– ጥቅም የለውም ብዬ ነው…
– ም…ኑ..
– እንዲህ ሆነሸ ማውራቱ….
– እና..ውራ…ማውራት አይደል የፈለግከው…እናውራ…
– ግዴለም ነገ ይደርሰል…
– አይ…ሆ…ን…ም አሁን እናውራ…
– ቤዚ…ይቅር
– አይ…ቀርም…እናውራ…እናወ…..ራ….
እንደለቅሶ ይሰራት ጀመር። ቤዚዬ….
– እሺ አልኳት እንዳታለቅስ…
– እሺ…ልጅቷ…እንዴት ነበረች…ጎበዝ ናት…..?
– ማ? አልኩኝ ደንገጥ ብዬ..
– እናውራ አላልክም…እናውራ….ያቺ አብረሃት የተኛሃት ልጅ…ጎበዝ ናት….ማለት…ከኔ ትበልጣለች?
ዝም አልኳት።
– ንገረኛ! እንዴት ነበረች…ትበልጠኛለች…..? ለቅሶ ጀመረች።
አቀፍኳት።
– ንገረኝ…..በለጠችኝ…ደስ አለችህ…ጎበዝ….
– ተይ ተይ በቃ…ቤዚዬ…ይቅርታ…በቃ…ይቅርታ አታልቅሺ አልኩና አጥብቄ አቅፌ ፀጉሯ ላይ…አይኖችዋን አፈራርቄ ሳምኳቸው።
– አትሳመኝ….ብላ ተፈናጥራ ተነሳች።
– እ?
– አትሳመኝ….እሷን በሳምክበት አፍ አትሳመኝ….ሚ..ኪ….ከሁሉ ሚያሳዝነኝ ምን እንደሆን ታውቃለህ…..አለችኝ ተመልሳ እየተቀመጠች።
ዝም አልኩ።
ቀጠለች-
– እወድሃለሁ…ማለቴ…ካላንተ ወንድ አልፈልግም…ጓደኞቼም ቤተሰቦቼም ቢመክሩኝም ባንተ መጨከን አቃተኝ…ሳምሪ ወንድ ልጅ አንዴ ከተልከሰከሰ ሁሌም ይልከሰከሳል…ይቅር ካልሽው እንደ ፈቃድ ነው ሚወስደው…ይቅርብሽ ብላኝ ነበር…ይሄን ታውቃለህ? እህቶቼ ለአይን ጠልተውሃል…እማዬማ ቤቴ አይምጣ ብላለች…እኔ ግን እወድሃለሁ…ልቤን ቢያመኝም…እወድሃለሁ…
– እነሱን ተያቸወ…አንቺ ከወደድሽኝ የኔ ጉዳይ ካንቺ ነው….አልኩ ፈጠን ብዬ…
– አይደለማ…..እወድሃለሁ ግን
👍12❤1
ውስጤ ቆስሏል…ባልድንስ…ከንፈርህን ባየሁት ቁጥር እንዴት እንደሳምካት ነው የማስበው….ከእሷ ጋር የተኛኸውን..አተ..አተ…አተኛ..ኘት..ኘት እያሰብኩ እንዴት አብሬህ እተኛለሁ….ደሞ….ደሞ እንዴት ብዬ ወደፊት አምንሃለሁ…
ተስፋ በመቁረጥ ዝም አልኩ። የማያቋርጠው ቅጣቴ ምንጭ አሁን ተገለፀልኝ። ፍቅሯን ባላጣም የእምነት ድልድዩን እንዳይጠገን አድርጌ ሰብሬዋለሁ። ከእንግዲህ እንደማዘር ቴሬሳ መልካም ሰው ብሆን ባጠፋሁት ጥፋት እንጂ በንጽህናዬ አልመዘንም። እንደ ጋንዲ ሩህሩህ ብሆን…ስረገጥ እኖራለሁ እንጂ አልከበርም። ግራ ጉንጬን ስሰጥ ቀኝ ጉንጬን በቡጢ ስደበደብ እኖራለሁ እንጂ ይቅር አልባልም።
ቤዛ ስኳሯ ተባብሶ ቃላቶቿ በማይገባኝ ደረጃ ሲጠባበቁ፣ ሰውነቷ ሲዝል ስብስብ አድርጌ አነሳኋትና አስተኛኋት።
ለብዙ ደቂቀዎች አጠገቧ ተቀምጬ ቆየሁና ጥልቅ እንቅልፍ ሲወስዳት ግንባሯን ሳምኩት።
ተገላበጠችና….፣ – ወንድ ልጅ አንዴ…አንዴ ከተልከሰከሰ ሁሌ ልክስክስ ነው…ብላ አጉረመረመች።
መለያየት አለብን የመጨረሻ ውሰኔ።
💫አለቀ💫
Like👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
አዳዲስ ድርሰቶችን ቶሎ ቶሎ ይዘን እንድንመጣ
ሁላችሁም 👍 like እያረጋቹ
አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን
ተስፋ በመቁረጥ ዝም አልኩ። የማያቋርጠው ቅጣቴ ምንጭ አሁን ተገለፀልኝ። ፍቅሯን ባላጣም የእምነት ድልድዩን እንዳይጠገን አድርጌ ሰብሬዋለሁ። ከእንግዲህ እንደማዘር ቴሬሳ መልካም ሰው ብሆን ባጠፋሁት ጥፋት እንጂ በንጽህናዬ አልመዘንም። እንደ ጋንዲ ሩህሩህ ብሆን…ስረገጥ እኖራለሁ እንጂ አልከበርም። ግራ ጉንጬን ስሰጥ ቀኝ ጉንጬን በቡጢ ስደበደብ እኖራለሁ እንጂ ይቅር አልባልም።
ቤዛ ስኳሯ ተባብሶ ቃላቶቿ በማይገባኝ ደረጃ ሲጠባበቁ፣ ሰውነቷ ሲዝል ስብስብ አድርጌ አነሳኋትና አስተኛኋት።
ለብዙ ደቂቀዎች አጠገቧ ተቀምጬ ቆየሁና ጥልቅ እንቅልፍ ሲወስዳት ግንባሯን ሳምኩት።
ተገላበጠችና….፣ – ወንድ ልጅ አንዴ…አንዴ ከተልከሰከሰ ሁሌ ልክስክስ ነው…ብላ አጉረመረመች።
መለያየት አለብን የመጨረሻ ውሰኔ።
💫አለቀ💫
Like👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
አዳዲስ ድርሰቶችን ቶሎ ቶሎ ይዘን እንድንመጣ
ሁላችሁም 👍 like እያረጋቹ
አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን
👍7🥰1
#ያመት_በአል_ማግስት_ትእይንቶች!!
- የተመጠጠ ቤት
የሞላ ሽንትቤት
ጭር ያለ ቤተሰብ
የተጠረገ ድስት -ድርቅ የመታው ሞሰብ!!
-ያደፈ ቄጤማ
በበግ በሰው እግር- የተደቀደቀ
ወዙ ባንድ ሌሊት -ተመጦ ያለቀ
መጥረጊያ ሚጠብቅ -ወድቆ ተበታትኖ
ትናንት ጌጥ የነበር- ዛሬ ጉድፍ ሆኖ!!
-የተወቀጠ ፊት -የነጋበት ድንገት
በዳንኪራ ብዛት-ወለም ያለው አንገት
የዞረበት ናላ -ጌሾ ያበከተው
እንኳንስ መገንዘብ -መጀዘብ ያቃተው
የወለቀ ወገብ -የዛለ ትከሻ
መኪና ይመስል -ብየዳ የሚሻ
-የጠጅና የጢስ- ድብልቅ እስትንፋስ
ከሆድ ሸለቆ ውስጥ -የታፈነ ነፋስ
ባንጀት የታሰረው
እንደተከበበ አመፀኛ ሽፍታ
መውጫ የቸገረው!
-የማይፈካ ሰማይ -የማይዘንብ ደመና
በላባና በፈርስ -ያደፈ ጎዳና
በበግ ራስ ምላስ -የተልከሰከሰ
የጠገበ ውሻ-
በመንፈቅ አንድ ጊዜ አጥንት የቀመሰ::
ሀንጎቨር ያዛገው-መሂና አሽከርካሪ
እግረኛ አስደንባሪ
በከፊል የነቃ -በከፊል የተኛ
ከሱ የማይሻል- የመኪና እረኛ
ካውራ ጎዳናው ዳር -ቁሞ ሚያንቀላፋ
ድብርትን ባናቱ -እንደ ቆብ የደፋ!!
The moral of the story :
የተድላ ማገዶ!!
ላጭር ጊዜ ነዶ
ላጭር ጊዜ ደምቆ
ላጭር ጊዜ ሙቆ
አመዱ ብዙ ነው: አያልቅም ተዝቆ!!
🔘በውቀቱ ስዩም🔘
- የተመጠጠ ቤት
የሞላ ሽንትቤት
ጭር ያለ ቤተሰብ
የተጠረገ ድስት -ድርቅ የመታው ሞሰብ!!
-ያደፈ ቄጤማ
በበግ በሰው እግር- የተደቀደቀ
ወዙ ባንድ ሌሊት -ተመጦ ያለቀ
መጥረጊያ ሚጠብቅ -ወድቆ ተበታትኖ
ትናንት ጌጥ የነበር- ዛሬ ጉድፍ ሆኖ!!
-የተወቀጠ ፊት -የነጋበት ድንገት
በዳንኪራ ብዛት-ወለም ያለው አንገት
የዞረበት ናላ -ጌሾ ያበከተው
እንኳንስ መገንዘብ -መጀዘብ ያቃተው
የወለቀ ወገብ -የዛለ ትከሻ
መኪና ይመስል -ብየዳ የሚሻ
-የጠጅና የጢስ- ድብልቅ እስትንፋስ
ከሆድ ሸለቆ ውስጥ -የታፈነ ነፋስ
ባንጀት የታሰረው
እንደተከበበ አመፀኛ ሽፍታ
መውጫ የቸገረው!
-የማይፈካ ሰማይ -የማይዘንብ ደመና
በላባና በፈርስ -ያደፈ ጎዳና
በበግ ራስ ምላስ -የተልከሰከሰ
የጠገበ ውሻ-
በመንፈቅ አንድ ጊዜ አጥንት የቀመሰ::
ሀንጎቨር ያዛገው-መሂና አሽከርካሪ
እግረኛ አስደንባሪ
በከፊል የነቃ -በከፊል የተኛ
ከሱ የማይሻል- የመኪና እረኛ
ካውራ ጎዳናው ዳር -ቁሞ ሚያንቀላፋ
ድብርትን ባናቱ -እንደ ቆብ የደፋ!!
The moral of the story :
የተድላ ማገዶ!!
ላጭር ጊዜ ነዶ
ላጭር ጊዜ ደምቆ
ላጭር ጊዜ ሙቆ
አመዱ ብዙ ነው: አያልቅም ተዝቆ!!
🔘በውቀቱ ስዩም🔘
#የመጀመሪያዋ_ግብዣ
ምድርም ሰማይም ባዶ እንደነበሩ ነው ድሮ ! …እና ባዶው ምድር ላይ …እግዚአብሔር ሳር ነሽ ቅጠል ነሽ ውሃ ነሽ ፀሃይ ነሽ እንደጉድ ፈጠረው ….
በግ ነሽ... ዶሮ ነሽ... በሬ ነሽ... ዳይኖሰር ነሽ …..ፈጠረ ፈጠረና ከዳር እስከ ዳር አየት አድርጎ ሲያበቃ ‹‹ፓ መልካም ነው ›› አለ ! ከዙፋኑ በታላቅ ግርማ ሞገስ ተነስቶ ወደፈጠረው ምድር እጁን ዘረጋ …..እናም ትኩሱን አፈር ቆንጠር አድርጎ ትንፋሹን እፍ ቢልበት ሰው ሁኖ እርፍ ! ያውም አዳምን የመሰለ ጎምላላ ትካሻ ከባድ ሰው !!
‹‹ ያውልህ በተዘጋጀ ምድር ላይ ዘና ብለህ ኑር ….›› አለው #አዳምን
ምን ዋጋ አለው አዳም ነጭናጫ ነበር ….እግዜር ብቅ ብሎ ‹‹ እንዴት ነው ኑሮ›› ሲለው
አዳም ይነጫነጫል ‹‹ ምን ኑሮ ……… ሳር ቅጠል ውሃ …ተራራ.. ሸንተረር ጫካ ዝሆን ዳይኖሰር ወፍ ወንዝ ዥረት ይሄ ሁሉ ኮተት ገና በፈጠርከኝ በሳምንቱ ደበረኝ ›› …..
‹‹ ጥሩ ! ምን ልፍጠርልህ ታዲያ ›› አለ እግዚአብሔር የሆዱን በሆዱ ይዞ ….መቸስ የሚጠቅመንን ነገር ቢያውቀውም ሰዎችን መጠየቅ ልማዱ ነው መሻታችን በፈቃዳችን ይሆን ዘንድ ይፈልጋልና
‹‹ እኔ ምን አውቄ ብትችል እንደገና ወደአፈር ብትመልሰኝ ›› ሲል አዳም ተነጫነጨ ተማረረ ….የአዳም መነጫነጭ መነሻው የእናት ፍቅር አለማውቁ የእናት ጡት ወተትም ሳይጠባ ማደጉ እደሆነ ይጠረጠራል …
እና እግዚአብሔር ሄዋንን አሰበ …አሰበ ማለት ያው ፈጠረ ነው ….ሒዋን ሁለት ተልእኮ ነበራት አንድም እናት ለሌለው የቲም ወንድ የእናት ፍቅር መስጠት …ሁለትም ሚስት ሁና አዳምን በስጋም በነፍስም ሙሉ ማድረግ ….ለዛ እኮ ነው በእያንዳንዷ ባፈቀርናት ሴት ውስጥ ትንሽ እናትነት ትንሽ እህትነት ብዙ ሚስትነት ተቀላቅሎ የሚገኘው ….ለዛ እኮ ነው የሴቶች እቅፍ የሴቶች ጠረን የሴቶች ድምፅ እና አብሮነት ከባድ ምቾት ውስጥ የሚሞጅረን !
ፍቅረኛችን ፍቅረኛ ብቻ ስትሆንኮ ትደብረናለች …እናት ብቻም ስትሆን ምቾት ነው የሚነሳን ….ቅመማ ቅመሙ እናትነት እህትነትና ሚስትነት አብሮ ሲቀመም ነው ደገፍ የምንላት ምቹ የነፍስ አጋር በነብሳችን ራስጌ ትራስ መከዳ ሁና በምቾት ቀና የምታደርገን …. ወንዶች ብዙ ጊዜ በፍቅር ትንታ የሚሞቱት ይህን ትራሳቸውን እያጡ እኮ ነው …. ይችን ያልተቀመመች ሴት እየተደገፉ ….አቤት ስትጎረባብጥ ….ከማይመች ፍቅር በኋላ ማጅራትህን ነው ስትራፖ የሚጨመድድህ …. ለምን መሰል ታዲያ ወንዶች ሴት ባዩ ቁጥር ወዳኋላ ወደጎን አንገታቸውን የሚያዞሩት …..ያሉበት ትራስ አልመች ቢላቸው ነው ወይም የተሸለ ትራስ ፍለጋ ……
(ሴቶች #የሚያሙን ሌላ ነው የአይን አመል ምናምን ነው ይላሉ ) እንግዲህ ሴትን ከአዳም ጎን አጥንት ሰራና ሲቀምማት ትንሽ እናትነት ትንሽ እህትነት በዛ ያለ ሚስትነት ለከለር ደግሞ ትንሽ ጓደኝነት ነስነስ አደረገባት ….በቃ ሴት ሆነች ኬክ የሆነች ሴት …!!
ሰነባብቶ እግዜር አዳምን ጠራና ‹‹ እህ እንዴት ነው ሂወት ? ›› ሲለው
‹‹ ኧረ ተወኝ ! አሁን ገና ገነትን ሙሉ አደረካት ›› ብሎ እግዜርን በሳቅ ሊገለው (ያው ድሮ አዳምና እግዚአብሄር እንዲህ ነበር በወዳጅነት የሚያወሩት ) እንግዲህ ሂዋን አዳም ጋር ወዲያ ወዲህ እያለች ስለወደፊቱ ብቻ እያወሩ(ያው ኑሮን ከመሃል ስለጀመሩት ትዝታ አልነበራቸውም ) በደስታ ፍንክንክ ብላ ስትኖር አንድ ቀን እንዲሁ ብቻዋን ወደጫካው ጎራ አለች …
እባብ እያፏጨ ቁሞ ነበር …ሂዋንን ሲያያት እንዲህ አላት
‹‹ ሃይ ቆንጅት እዚህ ሰፈር ነሽ እንዴ ? ››
‹‹ አዎ አንተስ ?››
‹‹ እኔም እዚሁ ነኝ …አንችን የመሰልሽ ቆንጆ ግን እንዴት እዚህ ጫካ ውስጥ ያስቀምጥሻል ….. ? እኔ እንዳንቺ አማላይና ውብ እግሮች ቢኖረኝ ኖሮ የት በደረስኩ››
ሂዋን ለመጀመሪያ ጊዜ አካባቢዋን ቃኘችው የተሸለ ሰፈር ይኖር ይሆን እንዴ ብላ ነፍሷን አባነነችው …..በዛ ላይ አዳም ራሱ ‹‹ቆንጆ›› አያውቅም ‹‹ውብ እግሮች እንዳላት›› ዛሬ ገና መስማቷ ነው …. እግሮቿን አየቻቸው ሂጅ ሂጅ አላት …. አድናቆቱ ጣማት ! በዛ ላይ አክብሮቱ ….መፅሃፉ ‹‹እባብ እግዜር ከፈጠራቸው ፍጥረታት ሁሉ ተንኮለኛው ነበር ›› ሲል ሄዋን
‹‹ ግን ምናይነት ፀዳ ያለ ለሴት ልጅ አክብሮት ያለው ፍጥረት ነው ›› ስትል አሰበች!
‹‹ እስኪ ሳር ቅጠል እንበል የኔ ቆንጆ ›› አላት እባብ …ያኔ ሳር ቅጠል እንበል ማለት በአሁኑ ቋንቋ ‹‹ሻይ ቡና እንበል›› እንደማለት ነው…እናም ሴት ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ግብዣ የተጋበዘችው የዛን ጊዜ ነው ….(ከዛ ጊዜ ጀምሮ ሴቶች ሻይ ቡና እንበል በሚል ግብዣ ከሻይ ቡና አልፈው ሌላ ታሪክ ውስጥ መግባት እንደጀመሩ የታሪክ ድርሳናት ይናገራሉ)
እንግዲህ ሂዋን በእባብ ተጋብዛ ግብዣው መዘዝ መዘዘና አዳምንም ይዞት ዘጭ አለ
‹‹ አዱሻ የማውቃት ዛፍ አለች አሪፍ ነገር ልጋብዝህ ›› አለችው ተከትሎ ሂዶ እጣ ፋንታውን ገመጠ ! በሰውኛ ሂሳብ ስናየው በሰው ልጅ ታሪክ ወንድን ለመጀመሪያ ጊዜ የጋበዘችው ደግሞ ሄዋን ናት(ግብዣ ድሮ ቀረ… የዛሬ ሴቶች በናታቸው አልወጡም ግብዣ ላይ ሂሂሂ )
አዳም ፍሬውን ሲበላ መብላትን መሰረት ያደረጉ ሁለት ርግማኖችን ተረገመ
‹‹አዳም›› አለው እግዜር
‹‹ አቤት ›› አለ እየፈራ
‹‹ግረህ ጥረህ ብላ …(ሄዋንን ግን በምግብ ጉዳይ አረገማትም ምናልባት በግብዣ እንድትኖር ሳይሆን አይቀርም የሚሉ አሉ)
ሁለተኛው እርግማንም ያው መብላት ጋር የተያያዘ ነው ……
‹‹ አዳም ቅድም ግረህ ጥረህ ብላ ብየሃለሁ አይደል ….?.››
‹‹አዎ ›› አለ ምን ሊለኝ ነው ብሎ በጉጉት እየጠበቀ ‹‹ አሁን ደግሞ እለሃለሁ …… አፈር ብላ ›› በቃ ትሞታለህ እንደማለት !
አዳም ግሮ ጥሮ ሲበላ ሄዋንን ግሮ ጥሮ ሲጋብዝ ይሄው እስካሁንም ሴትን መጋበዝ የአዳም
‹‹ሆቢ ›› ሁኖ ቀረ አፈር እስኪበላ ይጋብዛል ….በነገራችን ላይ ፊትህ የቆመ የተራበ ሚስኪን ሽ ጊዜ እጁን እየዘረጋ ምፅዋት ሲለምንህ እንዳላየህ አልፈህ ….. አንዷን ሴት ለምነህ ‹‹አፈር ስሆን›› ብለህ የምትጋብዘው ለምን ይመስለሃል ….እንደውም ግብዣ የተጀመረው ሴት ልጅ ከተቀመመችበት ቅመሞች አንዱን እናትነትን ከጣለችው በኋላ ነው …. አንተ የጎደለ ሆድ ፒዛ በርገር ቦንቦሊኖ ትጋብዛለህ የጎደለ መንፈስ ዘላለም ያዛጋል ! ለዛ እኮ ነው እናትነት የሚባለው ቅመም በተለይ ከተሜው ሴት ላይ ድራሹ የጠፋው ….እናት ሁልጊዜም ምን አንደምታደርግልህ እንጅ ምን እንደምታደርግላት አታስብም …ብታደርግላትም ፍቅሯ አይጨምርም ባታደርግላትም ፍቅሯ አይቀንስም … ዋናው ቅመም ሲከሽፍ ከቦንቦሊኖ ጋባዥ አንተ ፒዛ ጋባዥ እሱ የፍቅር ሃዋሪያ ተደርጎ በሚስትህ አይን ሲቀማጠል ብታይ እንዳይገርምህ !
እና በ ‹‹ግረህ ጥረህ ብላ›› እና ‹‹ በአፈር ብላ›› መሃል ….ኑሮ የሚባል ሂደት ተዘረጋ …..አዳም ሆድ እንዳይብሰው የተቀማትን ዘላለም ያስታውሳት ዘንድ በቀናት መካከል …በልፋቶች መሃል አንዲት አጭር ዘላለም….. አንዲት ቅልብጭ ያለች ረፍት አስቀመጠለት
….አዳም ታዲያ ለውዱ እንዲህ ይላታል
‹‹ ውዴ ነይ ልጋብዝሽ ….የእናትነት …የእህትነት የሚስትነት ቅመሞችሽን ይዘሽልኝ ነይ …………ነይ
ነ……..ይ ውዴ በአጭር ዘላለማችን አጭር ገነትን በነፍሳችን ጊዮን ዳርቻ ላይ እንመስርት …. !!
ምድርም ሰማይም ባዶ እንደነበሩ ነው ድሮ ! …እና ባዶው ምድር ላይ …እግዚአብሔር ሳር ነሽ ቅጠል ነሽ ውሃ ነሽ ፀሃይ ነሽ እንደጉድ ፈጠረው ….
በግ ነሽ... ዶሮ ነሽ... በሬ ነሽ... ዳይኖሰር ነሽ …..ፈጠረ ፈጠረና ከዳር እስከ ዳር አየት አድርጎ ሲያበቃ ‹‹ፓ መልካም ነው ›› አለ ! ከዙፋኑ በታላቅ ግርማ ሞገስ ተነስቶ ወደፈጠረው ምድር እጁን ዘረጋ …..እናም ትኩሱን አፈር ቆንጠር አድርጎ ትንፋሹን እፍ ቢልበት ሰው ሁኖ እርፍ ! ያውም አዳምን የመሰለ ጎምላላ ትካሻ ከባድ ሰው !!
‹‹ ያውልህ በተዘጋጀ ምድር ላይ ዘና ብለህ ኑር ….›› አለው #አዳምን
ምን ዋጋ አለው አዳም ነጭናጫ ነበር ….እግዜር ብቅ ብሎ ‹‹ እንዴት ነው ኑሮ›› ሲለው
አዳም ይነጫነጫል ‹‹ ምን ኑሮ ……… ሳር ቅጠል ውሃ …ተራራ.. ሸንተረር ጫካ ዝሆን ዳይኖሰር ወፍ ወንዝ ዥረት ይሄ ሁሉ ኮተት ገና በፈጠርከኝ በሳምንቱ ደበረኝ ›› …..
‹‹ ጥሩ ! ምን ልፍጠርልህ ታዲያ ›› አለ እግዚአብሔር የሆዱን በሆዱ ይዞ ….መቸስ የሚጠቅመንን ነገር ቢያውቀውም ሰዎችን መጠየቅ ልማዱ ነው መሻታችን በፈቃዳችን ይሆን ዘንድ ይፈልጋልና
‹‹ እኔ ምን አውቄ ብትችል እንደገና ወደአፈር ብትመልሰኝ ›› ሲል አዳም ተነጫነጨ ተማረረ ….የአዳም መነጫነጭ መነሻው የእናት ፍቅር አለማውቁ የእናት ጡት ወተትም ሳይጠባ ማደጉ እደሆነ ይጠረጠራል …
እና እግዚአብሔር ሄዋንን አሰበ …አሰበ ማለት ያው ፈጠረ ነው ….ሒዋን ሁለት ተልእኮ ነበራት አንድም እናት ለሌለው የቲም ወንድ የእናት ፍቅር መስጠት …ሁለትም ሚስት ሁና አዳምን በስጋም በነፍስም ሙሉ ማድረግ ….ለዛ እኮ ነው በእያንዳንዷ ባፈቀርናት ሴት ውስጥ ትንሽ እናትነት ትንሽ እህትነት ብዙ ሚስትነት ተቀላቅሎ የሚገኘው ….ለዛ እኮ ነው የሴቶች እቅፍ የሴቶች ጠረን የሴቶች ድምፅ እና አብሮነት ከባድ ምቾት ውስጥ የሚሞጅረን !
ፍቅረኛችን ፍቅረኛ ብቻ ስትሆንኮ ትደብረናለች …እናት ብቻም ስትሆን ምቾት ነው የሚነሳን ….ቅመማ ቅመሙ እናትነት እህትነትና ሚስትነት አብሮ ሲቀመም ነው ደገፍ የምንላት ምቹ የነፍስ አጋር በነብሳችን ራስጌ ትራስ መከዳ ሁና በምቾት ቀና የምታደርገን …. ወንዶች ብዙ ጊዜ በፍቅር ትንታ የሚሞቱት ይህን ትራሳቸውን እያጡ እኮ ነው …. ይችን ያልተቀመመች ሴት እየተደገፉ ….አቤት ስትጎረባብጥ ….ከማይመች ፍቅር በኋላ ማጅራትህን ነው ስትራፖ የሚጨመድድህ …. ለምን መሰል ታዲያ ወንዶች ሴት ባዩ ቁጥር ወዳኋላ ወደጎን አንገታቸውን የሚያዞሩት …..ያሉበት ትራስ አልመች ቢላቸው ነው ወይም የተሸለ ትራስ ፍለጋ ……
(ሴቶች #የሚያሙን ሌላ ነው የአይን አመል ምናምን ነው ይላሉ ) እንግዲህ ሴትን ከአዳም ጎን አጥንት ሰራና ሲቀምማት ትንሽ እናትነት ትንሽ እህትነት በዛ ያለ ሚስትነት ለከለር ደግሞ ትንሽ ጓደኝነት ነስነስ አደረገባት ….በቃ ሴት ሆነች ኬክ የሆነች ሴት …!!
ሰነባብቶ እግዜር አዳምን ጠራና ‹‹ እህ እንዴት ነው ሂወት ? ›› ሲለው
‹‹ ኧረ ተወኝ ! አሁን ገና ገነትን ሙሉ አደረካት ›› ብሎ እግዜርን በሳቅ ሊገለው (ያው ድሮ አዳምና እግዚአብሄር እንዲህ ነበር በወዳጅነት የሚያወሩት ) እንግዲህ ሂዋን አዳም ጋር ወዲያ ወዲህ እያለች ስለወደፊቱ ብቻ እያወሩ(ያው ኑሮን ከመሃል ስለጀመሩት ትዝታ አልነበራቸውም ) በደስታ ፍንክንክ ብላ ስትኖር አንድ ቀን እንዲሁ ብቻዋን ወደጫካው ጎራ አለች …
እባብ እያፏጨ ቁሞ ነበር …ሂዋንን ሲያያት እንዲህ አላት
‹‹ ሃይ ቆንጅት እዚህ ሰፈር ነሽ እንዴ ? ››
‹‹ አዎ አንተስ ?››
‹‹ እኔም እዚሁ ነኝ …አንችን የመሰልሽ ቆንጆ ግን እንዴት እዚህ ጫካ ውስጥ ያስቀምጥሻል ….. ? እኔ እንዳንቺ አማላይና ውብ እግሮች ቢኖረኝ ኖሮ የት በደረስኩ››
ሂዋን ለመጀመሪያ ጊዜ አካባቢዋን ቃኘችው የተሸለ ሰፈር ይኖር ይሆን እንዴ ብላ ነፍሷን አባነነችው …..በዛ ላይ አዳም ራሱ ‹‹ቆንጆ›› አያውቅም ‹‹ውብ እግሮች እንዳላት›› ዛሬ ገና መስማቷ ነው …. እግሮቿን አየቻቸው ሂጅ ሂጅ አላት …. አድናቆቱ ጣማት ! በዛ ላይ አክብሮቱ ….መፅሃፉ ‹‹እባብ እግዜር ከፈጠራቸው ፍጥረታት ሁሉ ተንኮለኛው ነበር ›› ሲል ሄዋን
‹‹ ግን ምናይነት ፀዳ ያለ ለሴት ልጅ አክብሮት ያለው ፍጥረት ነው ›› ስትል አሰበች!
‹‹ እስኪ ሳር ቅጠል እንበል የኔ ቆንጆ ›› አላት እባብ …ያኔ ሳር ቅጠል እንበል ማለት በአሁኑ ቋንቋ ‹‹ሻይ ቡና እንበል›› እንደማለት ነው…እናም ሴት ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ግብዣ የተጋበዘችው የዛን ጊዜ ነው ….(ከዛ ጊዜ ጀምሮ ሴቶች ሻይ ቡና እንበል በሚል ግብዣ ከሻይ ቡና አልፈው ሌላ ታሪክ ውስጥ መግባት እንደጀመሩ የታሪክ ድርሳናት ይናገራሉ)
እንግዲህ ሂዋን በእባብ ተጋብዛ ግብዣው መዘዝ መዘዘና አዳምንም ይዞት ዘጭ አለ
‹‹ አዱሻ የማውቃት ዛፍ አለች አሪፍ ነገር ልጋብዝህ ›› አለችው ተከትሎ ሂዶ እጣ ፋንታውን ገመጠ ! በሰውኛ ሂሳብ ስናየው በሰው ልጅ ታሪክ ወንድን ለመጀመሪያ ጊዜ የጋበዘችው ደግሞ ሄዋን ናት(ግብዣ ድሮ ቀረ… የዛሬ ሴቶች በናታቸው አልወጡም ግብዣ ላይ ሂሂሂ )
አዳም ፍሬውን ሲበላ መብላትን መሰረት ያደረጉ ሁለት ርግማኖችን ተረገመ
‹‹አዳም›› አለው እግዜር
‹‹ አቤት ›› አለ እየፈራ
‹‹ግረህ ጥረህ ብላ …(ሄዋንን ግን በምግብ ጉዳይ አረገማትም ምናልባት በግብዣ እንድትኖር ሳይሆን አይቀርም የሚሉ አሉ)
ሁለተኛው እርግማንም ያው መብላት ጋር የተያያዘ ነው ……
‹‹ አዳም ቅድም ግረህ ጥረህ ብላ ብየሃለሁ አይደል ….?.››
‹‹አዎ ›› አለ ምን ሊለኝ ነው ብሎ በጉጉት እየጠበቀ ‹‹ አሁን ደግሞ እለሃለሁ …… አፈር ብላ ›› በቃ ትሞታለህ እንደማለት !
አዳም ግሮ ጥሮ ሲበላ ሄዋንን ግሮ ጥሮ ሲጋብዝ ይሄው እስካሁንም ሴትን መጋበዝ የአዳም
‹‹ሆቢ ›› ሁኖ ቀረ አፈር እስኪበላ ይጋብዛል ….በነገራችን ላይ ፊትህ የቆመ የተራበ ሚስኪን ሽ ጊዜ እጁን እየዘረጋ ምፅዋት ሲለምንህ እንዳላየህ አልፈህ ….. አንዷን ሴት ለምነህ ‹‹አፈር ስሆን›› ብለህ የምትጋብዘው ለምን ይመስለሃል ….እንደውም ግብዣ የተጀመረው ሴት ልጅ ከተቀመመችበት ቅመሞች አንዱን እናትነትን ከጣለችው በኋላ ነው …. አንተ የጎደለ ሆድ ፒዛ በርገር ቦንቦሊኖ ትጋብዛለህ የጎደለ መንፈስ ዘላለም ያዛጋል ! ለዛ እኮ ነው እናትነት የሚባለው ቅመም በተለይ ከተሜው ሴት ላይ ድራሹ የጠፋው ….እናት ሁልጊዜም ምን አንደምታደርግልህ እንጅ ምን እንደምታደርግላት አታስብም …ብታደርግላትም ፍቅሯ አይጨምርም ባታደርግላትም ፍቅሯ አይቀንስም … ዋናው ቅመም ሲከሽፍ ከቦንቦሊኖ ጋባዥ አንተ ፒዛ ጋባዥ እሱ የፍቅር ሃዋሪያ ተደርጎ በሚስትህ አይን ሲቀማጠል ብታይ እንዳይገርምህ !
እና በ ‹‹ግረህ ጥረህ ብላ›› እና ‹‹ በአፈር ብላ›› መሃል ….ኑሮ የሚባል ሂደት ተዘረጋ …..አዳም ሆድ እንዳይብሰው የተቀማትን ዘላለም ያስታውሳት ዘንድ በቀናት መካከል …በልፋቶች መሃል አንዲት አጭር ዘላለም….. አንዲት ቅልብጭ ያለች ረፍት አስቀመጠለት
….አዳም ታዲያ ለውዱ እንዲህ ይላታል
‹‹ ውዴ ነይ ልጋብዝሽ ….የእናትነት …የእህትነት የሚስትነት ቅመሞችሽን ይዘሽልኝ ነይ …………ነይ
ነ……..ይ ውዴ በአጭር ዘላለማችን አጭር ገነትን በነፍሳችን ጊዮን ዳርቻ ላይ እንመስርት …. !!
👍2🤔2
#ቲቸር_ጥጋቡ
አበበ በሶ በላ ….ጫላ ጩቤ ጨበጠ …ቲቸር ጥጋቡ …… ››
የአስራ ሁለተኛ ክፍል ስፖርት አስተማሪያችን ጋሽ ጥጋቡ እንደዛን ቀን ተበሳጭቶ አይተነው አናውቅም ! ሁልጊዜ ሰኞ በመጀመሪያው?ቨ ክፍለጊዜ ‹‹ስፖርት ›› ነበር የምንማረው ! ታዲያ ወንዶቹ ሁላችንም ደስተኞች ነበርን ! ሴቶቹ ግን ክላሱን አየወዱትም ! ምክንያቱም ቅዳሜና እሁድ ፀጉራቸውን ተተኩሰው ጥፍራቸውን በጥፍር ቀለም አስውበው ‹‹ዩኒፎርማቸውን›› አጥበውና ተኩሰው ሰኞ አበባ መስለው የሚመጡት ሴቶች እዛ ሜዳ ላይ ‹‹ተኙ ተንከባለሉ ሩጡ ዝለሉ ›› ሲባሉ ውለው ፀጉራቸው ተንጨባሮና ሳርና ሌላም ሸቀጥ ተሸክሞ ላብ በላብ ሁነው ሰኟቸውን መጀመር አስከፊ አይፈልጉም ነበር !
እንደውም አንዳንዴ ስፖርት ላለመስራት ‹‹ቲቸር ማንስትሬሽን ላይ ነኝ›› ብለው የሚያስፈቅዱ ሴቶችን ‹‹አ…ይ በየሰማንቱ ነው እንዴ የእናተ ….›› ብሎ ይቆጣቸዋል ! በእርግጥ ቲቸር ጨካኝ አልነበረም ግን የሴቶች ስፖርት መጥላት ያበሳጨው ነበር! አንድ ቀን ታዲያ ‹‹ እራስን ከአደጋ መከላለከል ›› የሚል የማርሻል አርት አንድ ክፍል የሆነ ትምህርት እያስተማረን ነበር…. ትምህርቱ ስለሚያዝናና በተለይ ወንዶቹ ደስ ብሎን ነበር የምንሰራው ! ተሰልፈን ያ….ሄይ….. ሁ እንላለን ! ሴቶቹም ድምፃቸውን ቀንሰው ኤጭ ! ይላሉ !
‹‹ ለምሳሌ ጩቤ የያዘ ሰው አይኑን አፍጥጦ ሊያጠቃችሁ ፊት ለፊታችሁ ቢቆም ምን ታደርጋላችሁ ›› ብሎ ጠየቀን ቲቸር
‹‹መጀመሪያ አማትባለሁ ›› አለ ፍቅረ ማርቆስ ሁላችንም ሳቅን
‹‹ደህና ድንጋይ ፈልጌ እፈነክተዋለሁ ›› አለ ታደሰ የሚባል የክላሳችን ልጅ
‹‹ አግሬ አውጭኝ ብሎ ፈትለክ ነው ወደኋላ ›› ይላል ሌላው ! ቲቸር ግን እንዴት ጩቤውን አንደምናስጥለው በምሳሌ አንድ ልጅ ወደፊት አስወጥቶ አሳየን ! ቲቸር ‹‹ለምሳሌ የሚሆን አንድ ሰው ወደፊት ይምጣ እስኪ ›› ሲል ሁላችንም ፈርተን ዝም ነበር ያልነው ቲቸር ራሱ አንዱን ጠራው እና ተማሪውን እስክርቢቶ እንደጩቤ አስይዞ አንዴት ማስጣል እንደሚቻል አሳየን !
‹‹ በመጀመሪያ ሊያጠቃችሁ የመጣው ሰው እንኳን ጩቤ ጎራዴ ቢየዝ እንዳትፈሩ እንዳትደነግጡ ተረጋግታችሁ አያያዙን ተመልከቱ ‹ አያያዙን አይተህ ጭብጦውን ቀማው › አይደለ ተረቱ ….ከዛ እንዲህ እጁን አንጓው ላይ በፍጥነት ትይዙና ወደግራ እጁን ጠምዝዛችሁ …..ልክ እንደዚህ ያ …ሁይ ›› ብሎ ለምሳሌ የወጣውን ልጅ መሬት ላይ በጀርባው ዘረጋውና እና የያዘውን ቢክ እስክርቢቶ አስጣለው ! ቲቸር ጎበዝ ነበር ! (#በነገራችን ላይ ዱርየወች ቲቸርን ማታ ላይ በጩቤ አስፈራርተው ላፕቶፑን እንደቀሙት ቆይቶ ዩኒቨርስቲ ከገባን በኋላ ሰምተናል ‹የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም› )
ቀጥሎ ሴቶች እራሳቸውን ከጥቃት እንዴት እንደሚከላከሉ ማስተማር ጀመረ
‹‹ ሊሊ ››
‹‹የስ ቲቸር ›› አለች ሞልቃቃዋና ቆንጆዋ የክላሳችን ልጅ ›› የሊሊ ቁንጅና መቸም ተአምር ነው በቃ ተአምር !
ቲቸር ቀጠሉ ‹‹ለምሳሌ አንድ ወንድ አስገድዶ ሊደፍርሽ ቢሞክር እንበል ….››
‹‹ኦ ማይ ጋድ ›› አለች ሊሊ ቲቸር ሳይጨርሱት ቀድማ !
‹‹ ምሳሌ ነው …እንዴት እንደምትከላከይው በምሳሌ እናያለን ….›› ብሎ ሊሊን ወደፊት አስወጣትና ወደእኛ ዙሮ ‹‹ እስቲ አንድ ወንድ እንደሊሊ ደፋሪ ሁኖ ምሳሌውን የማሳይበት ሲል ›› ሁላችንም ወንዶቹ እጃችንን አውጥተን ወደፊት ተንደረደርን ! እንዴ ሊሊ ጋር ለምሳሌም ቢሆን መደፋፈር ፅድቅ ነበር ለእኛ ! ሊሊ እኮ ነች ! በተለይ እንዲህ ጥብቅብቅ ባለ ታይትና በጃፖኒ ቁማ ጡቶቿ ተቀስረው አስተማሪው ‹‹ኑ ድፈሯት ›› ሲል ማን ሞኝ አለ አርፎ የሚቆም ዘራፍ ! ምን ያደርጋል ‹‹ ተውት በቃ እራሴ አሳያችኋለሁ ›› አለና ኩም አደረገን ቲቸር !እግዜር ይይለት ! ‹‹….ምን አይነት ነገር ነው ተማሪ ተኮር ነው ትምህርቱ አልተባለም እንዴ ሁሉን ነገር አስተማሪው ብቻ ….›› ብያለሁ በሆዴ !
ቲቸር ሜዳው ላይ በጀርባው ተኛና ..‹‹ አሁን እኔ ደፋሪ ነኝ አንች ነይ እግርሽን ክፈችና ከላየ ሆዴ ላይ ውጭ ›› አላት
‹‹ እንዴ ቲቸር አልወጣም !›› አለች ሊሊ ፊቷን አጨፍግጋ !
‹‹ለምንድነው የማትወጭው››
‹‹ ከመቸ ወዲህ ነው ሴት ከላይ ሁና የምትደፈረው ›› አለች ሊሊ
‹‹ነይ ዝም ብለሽ ውጭ ››
‹‹አልወጣም ››
‹‹ ነግሪያለሁ ውጭ ››
‹‹እኔም ነገርኮዎት አልወጣም ቲቸር ደግሞ ከላይ ሁኖ መደፈር አለ እነ….ዴ …ሆሆ ››
‹‹ከላይ ሆንሽ ከታች ምን ለውጥ አለው ››
‹‹ ከላይ ከሆንኩማ ‹ኦልሬዲ› እራሴ ፈልጌ ነው ማለት ነው !! ምኑን ደፈራ ሆነ ቲቸር አልወጣብወትም ›› ብላ ቲቸር እንደተንጋለሉ ትታቸው ወደቦታዋ ተመለሰች !
ቲቸር በጣም ስለተበሳጩ ሊሊን ወላጅ አስጠሯት ! ወላጆቿ ቲቸርና ሊሊ የትምህርት ቤታችን ርእሰ መምህር ጋር ቀረቡ
ቲቸር የሊሊን ጥጋብና አስተማሪ መናቋን አስረዱ ….ሊሊ በበኩሏ ‹ሴት ከላይ ሁና ስትደፈር ታይቶም ተሰምቶም እንደማይታወቅ አስረዳች › የሊሊ ወላጆች ግራ ተጋብተው ዝም አሉ ….በመጨረሻም ርእሰ መምህሩ ውሳኔያቸውን አሳልፉ !
‹‹መምህር ጥጋቡ…. መቸም አንተ ምስጉን መምህራችን መሆንህን ማንም ያውቃል….. በሙያህም ጣልቃ መግባት የለብኝም ቢሆንም ተማሪወችን በሚወዱት መንገድ ማስተማር የተሸለ ትምህርቱን እንዲረዱት ያደርጋልና ካሁን በኋላ ከላይ ሁነህ በመድፈር አስተምራት …አንችም አርፈሽ አደፋፈሩን ተማሪ አንድ ቀን ይጠቅምሻል ››ሲሉ ሸኟቸው!😃
🔘በ አሌክስ አብርሀም🔘
አበበ በሶ በላ ….ጫላ ጩቤ ጨበጠ …ቲቸር ጥጋቡ …… ››
የአስራ ሁለተኛ ክፍል ስፖርት አስተማሪያችን ጋሽ ጥጋቡ እንደዛን ቀን ተበሳጭቶ አይተነው አናውቅም ! ሁልጊዜ ሰኞ በመጀመሪያው?ቨ ክፍለጊዜ ‹‹ስፖርት ›› ነበር የምንማረው ! ታዲያ ወንዶቹ ሁላችንም ደስተኞች ነበርን ! ሴቶቹ ግን ክላሱን አየወዱትም ! ምክንያቱም ቅዳሜና እሁድ ፀጉራቸውን ተተኩሰው ጥፍራቸውን በጥፍር ቀለም አስውበው ‹‹ዩኒፎርማቸውን›› አጥበውና ተኩሰው ሰኞ አበባ መስለው የሚመጡት ሴቶች እዛ ሜዳ ላይ ‹‹ተኙ ተንከባለሉ ሩጡ ዝለሉ ›› ሲባሉ ውለው ፀጉራቸው ተንጨባሮና ሳርና ሌላም ሸቀጥ ተሸክሞ ላብ በላብ ሁነው ሰኟቸውን መጀመር አስከፊ አይፈልጉም ነበር !
እንደውም አንዳንዴ ስፖርት ላለመስራት ‹‹ቲቸር ማንስትሬሽን ላይ ነኝ›› ብለው የሚያስፈቅዱ ሴቶችን ‹‹አ…ይ በየሰማንቱ ነው እንዴ የእናተ ….›› ብሎ ይቆጣቸዋል ! በእርግጥ ቲቸር ጨካኝ አልነበረም ግን የሴቶች ስፖርት መጥላት ያበሳጨው ነበር! አንድ ቀን ታዲያ ‹‹ እራስን ከአደጋ መከላለከል ›› የሚል የማርሻል አርት አንድ ክፍል የሆነ ትምህርት እያስተማረን ነበር…. ትምህርቱ ስለሚያዝናና በተለይ ወንዶቹ ደስ ብሎን ነበር የምንሰራው ! ተሰልፈን ያ….ሄይ….. ሁ እንላለን ! ሴቶቹም ድምፃቸውን ቀንሰው ኤጭ ! ይላሉ !
‹‹ ለምሳሌ ጩቤ የያዘ ሰው አይኑን አፍጥጦ ሊያጠቃችሁ ፊት ለፊታችሁ ቢቆም ምን ታደርጋላችሁ ›› ብሎ ጠየቀን ቲቸር
‹‹መጀመሪያ አማትባለሁ ›› አለ ፍቅረ ማርቆስ ሁላችንም ሳቅን
‹‹ደህና ድንጋይ ፈልጌ እፈነክተዋለሁ ›› አለ ታደሰ የሚባል የክላሳችን ልጅ
‹‹ አግሬ አውጭኝ ብሎ ፈትለክ ነው ወደኋላ ›› ይላል ሌላው ! ቲቸር ግን እንዴት ጩቤውን አንደምናስጥለው በምሳሌ አንድ ልጅ ወደፊት አስወጥቶ አሳየን ! ቲቸር ‹‹ለምሳሌ የሚሆን አንድ ሰው ወደፊት ይምጣ እስኪ ›› ሲል ሁላችንም ፈርተን ዝም ነበር ያልነው ቲቸር ራሱ አንዱን ጠራው እና ተማሪውን እስክርቢቶ እንደጩቤ አስይዞ አንዴት ማስጣል እንደሚቻል አሳየን !
‹‹ በመጀመሪያ ሊያጠቃችሁ የመጣው ሰው እንኳን ጩቤ ጎራዴ ቢየዝ እንዳትፈሩ እንዳትደነግጡ ተረጋግታችሁ አያያዙን ተመልከቱ ‹ አያያዙን አይተህ ጭብጦውን ቀማው › አይደለ ተረቱ ….ከዛ እንዲህ እጁን አንጓው ላይ በፍጥነት ትይዙና ወደግራ እጁን ጠምዝዛችሁ …..ልክ እንደዚህ ያ …ሁይ ›› ብሎ ለምሳሌ የወጣውን ልጅ መሬት ላይ በጀርባው ዘረጋውና እና የያዘውን ቢክ እስክርቢቶ አስጣለው ! ቲቸር ጎበዝ ነበር ! (#በነገራችን ላይ ዱርየወች ቲቸርን ማታ ላይ በጩቤ አስፈራርተው ላፕቶፑን እንደቀሙት ቆይቶ ዩኒቨርስቲ ከገባን በኋላ ሰምተናል ‹የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም› )
ቀጥሎ ሴቶች እራሳቸውን ከጥቃት እንዴት እንደሚከላከሉ ማስተማር ጀመረ
‹‹ ሊሊ ››
‹‹የስ ቲቸር ›› አለች ሞልቃቃዋና ቆንጆዋ የክላሳችን ልጅ ›› የሊሊ ቁንጅና መቸም ተአምር ነው በቃ ተአምር !
ቲቸር ቀጠሉ ‹‹ለምሳሌ አንድ ወንድ አስገድዶ ሊደፍርሽ ቢሞክር እንበል ….››
‹‹ኦ ማይ ጋድ ›› አለች ሊሊ ቲቸር ሳይጨርሱት ቀድማ !
‹‹ ምሳሌ ነው …እንዴት እንደምትከላከይው በምሳሌ እናያለን ….›› ብሎ ሊሊን ወደፊት አስወጣትና ወደእኛ ዙሮ ‹‹ እስቲ አንድ ወንድ እንደሊሊ ደፋሪ ሁኖ ምሳሌውን የማሳይበት ሲል ›› ሁላችንም ወንዶቹ እጃችንን አውጥተን ወደፊት ተንደረደርን ! እንዴ ሊሊ ጋር ለምሳሌም ቢሆን መደፋፈር ፅድቅ ነበር ለእኛ ! ሊሊ እኮ ነች ! በተለይ እንዲህ ጥብቅብቅ ባለ ታይትና በጃፖኒ ቁማ ጡቶቿ ተቀስረው አስተማሪው ‹‹ኑ ድፈሯት ›› ሲል ማን ሞኝ አለ አርፎ የሚቆም ዘራፍ ! ምን ያደርጋል ‹‹ ተውት በቃ እራሴ አሳያችኋለሁ ›› አለና ኩም አደረገን ቲቸር !እግዜር ይይለት ! ‹‹….ምን አይነት ነገር ነው ተማሪ ተኮር ነው ትምህርቱ አልተባለም እንዴ ሁሉን ነገር አስተማሪው ብቻ ….›› ብያለሁ በሆዴ !
ቲቸር ሜዳው ላይ በጀርባው ተኛና ..‹‹ አሁን እኔ ደፋሪ ነኝ አንች ነይ እግርሽን ክፈችና ከላየ ሆዴ ላይ ውጭ ›› አላት
‹‹ እንዴ ቲቸር አልወጣም !›› አለች ሊሊ ፊቷን አጨፍግጋ !
‹‹ለምንድነው የማትወጭው››
‹‹ ከመቸ ወዲህ ነው ሴት ከላይ ሁና የምትደፈረው ›› አለች ሊሊ
‹‹ነይ ዝም ብለሽ ውጭ ››
‹‹አልወጣም ››
‹‹ ነግሪያለሁ ውጭ ››
‹‹እኔም ነገርኮዎት አልወጣም ቲቸር ደግሞ ከላይ ሁኖ መደፈር አለ እነ….ዴ …ሆሆ ››
‹‹ከላይ ሆንሽ ከታች ምን ለውጥ አለው ››
‹‹ ከላይ ከሆንኩማ ‹ኦልሬዲ› እራሴ ፈልጌ ነው ማለት ነው !! ምኑን ደፈራ ሆነ ቲቸር አልወጣብወትም ›› ብላ ቲቸር እንደተንጋለሉ ትታቸው ወደቦታዋ ተመለሰች !
ቲቸር በጣም ስለተበሳጩ ሊሊን ወላጅ አስጠሯት ! ወላጆቿ ቲቸርና ሊሊ የትምህርት ቤታችን ርእሰ መምህር ጋር ቀረቡ
ቲቸር የሊሊን ጥጋብና አስተማሪ መናቋን አስረዱ ….ሊሊ በበኩሏ ‹ሴት ከላይ ሁና ስትደፈር ታይቶም ተሰምቶም እንደማይታወቅ አስረዳች › የሊሊ ወላጆች ግራ ተጋብተው ዝም አሉ ….በመጨረሻም ርእሰ መምህሩ ውሳኔያቸውን አሳልፉ !
‹‹መምህር ጥጋቡ…. መቸም አንተ ምስጉን መምህራችን መሆንህን ማንም ያውቃል….. በሙያህም ጣልቃ መግባት የለብኝም ቢሆንም ተማሪወችን በሚወዱት መንገድ ማስተማር የተሸለ ትምህርቱን እንዲረዱት ያደርጋልና ካሁን በኋላ ከላይ ሁነህ በመድፈር አስተምራት …አንችም አርፈሽ አደፋፈሩን ተማሪ አንድ ቀን ይጠቅምሻል ››ሲሉ ሸኟቸው!😃
🔘በ አሌክስ አብርሀም🔘
👍7😁2
#በቀኝ_አሳድረኝ
ቀጭ ….ቀጭቀጭ …ሲጥ ..ሲጥጥ
እህህህ ..‹‹ቀስ በል የኔ ጌ….ታ …››
በ ሹ ክ ሹ ክ ታ
ከግድግዳየ ወዲያ …
ሁሉም ባረፈበት ማታ
ካዲስ ተጋቢዎቹ ቤት
አልፎ የሚመጣ ንዝረት
ጆሮ የሚያቆም ወላፈን
ደምፃቸውን ለቀቅ ….አፈን
‹‹ውይይይይ ….›› የሷ ድምፅ …... በሲቃ ሲተን
የዝምታ አለት …. በፍቅር ፈንጅ… አልጋቸው ላይ
ሲበታተን
ደግሞ የሱ ከንፈር ዋይታ …….እ…..ሟ
የወንድ ልቡ ብረት ወኔው …በፍቅር እቶን
ሲሟሟ
‹‹እፉፉፉፉፉ ››ድምፃቸውን እንደጅራፍ ባንድ
ፈትለው ባንድ ገምደው
ድቅድቅ የጨለማን መንጋ በሲቃ ጩኸት አሳደው
ባንድ ላይ ሲቀላቀሉ የብቻን ግንብ ወዲያ ንደው
አውሎ እፎይታ
ከቀኝ ግድግዳየ ተጎራባች…. ሁሉ ባረፈበት ማታ
ዝምምምምምምታ !
ተኙ መሰል !!
* ** *
ሌላ ድምፅ ደግሞ ከግራ
በቆመ ጆሮየ ግርጌ ያልፋል ድሩን እያደራ
‹‹ እእእእእ ›› ይችኛይቱ ጎረቤቴ
እንዲህ በሙሉ ጨረቃ የሚያስቃዣት በሽተኛ
ሙሉ ሌሊት ስትዋትት ስትሰቃይ የማተኛ
ድፍን ሌሊት ስትዛብር ስታቃስት የሚነጋ
ሲጥ ሲጥጥ ወጉ እንዳይቀር የሷም አልጋ
ቀንም በመቀነቻ ነው … ወገቧን አስራ
የምትቆመው
የበሽታ ክፉ አካናድ ስጋዋን እየጎሰመው
በሁለት ቅስቻ መሃል … ግራ ቀኙኝ እያደመጥኩ
ካንዱ <ጆሮየ አውጭኝ> እያልኩ… ሌላውን
ባሳብ እያለምኩ
በመሃል የምኖር እኔ …
እንቅልፍ ሊጥለኝ ሲዳዳ በግዜር ላይ ቅኔ
እቀኛለሁ
የወጉን ፀሎት ሰም አድርጌ ‹‹በቀኝ አሳድረኝ
››እላለሁ
** **** ****
ኳኳኳኳኳኳኳኳኳኳ ኳ ኳ
አዲስ ተጋቢወች ማለዳ ተነስተው…. ለቁርስ
ቲማቲም እየቀጠቀጡ
ሲጥጥጥጥጥጥጥጥጥ
ታመው ያደሩቱ ቤተስኪያን ሊስሙ …..ከቤት
እየወጡ
በቀኝም በግራ እንዲህ የሚል ልሳን
‹‹ሰላም ያሳደርከን በሰላም አውለን ››
ይች ናት አገሬ … እኩል እግዚሃርን
የሚዘይሩባት… እኩል ያላደሩ
እኩል ቀን ጀማሪ እኩል ባልሆነ ቁርስ ተስፋ
እየቋጠሩ !
ከታች እስኪሾሙ ከላይ እስኪጠሩ !!
ከቀኝም ከግራም …መሃል ለሰፈሩ
ይች ናት አገሬ እንዲህ ነው አዳሩ !
🔘አሌክስ አብርሃም🔘
ቀጭ ….ቀጭቀጭ …ሲጥ ..ሲጥጥ
እህህህ ..‹‹ቀስ በል የኔ ጌ….ታ …››
በ ሹ ክ ሹ ክ ታ
ከግድግዳየ ወዲያ …
ሁሉም ባረፈበት ማታ
ካዲስ ተጋቢዎቹ ቤት
አልፎ የሚመጣ ንዝረት
ጆሮ የሚያቆም ወላፈን
ደምፃቸውን ለቀቅ ….አፈን
‹‹ውይይይይ ….›› የሷ ድምፅ …... በሲቃ ሲተን
የዝምታ አለት …. በፍቅር ፈንጅ… አልጋቸው ላይ
ሲበታተን
ደግሞ የሱ ከንፈር ዋይታ …….እ…..ሟ
የወንድ ልቡ ብረት ወኔው …በፍቅር እቶን
ሲሟሟ
‹‹እፉፉፉፉፉ ››ድምፃቸውን እንደጅራፍ ባንድ
ፈትለው ባንድ ገምደው
ድቅድቅ የጨለማን መንጋ በሲቃ ጩኸት አሳደው
ባንድ ላይ ሲቀላቀሉ የብቻን ግንብ ወዲያ ንደው
አውሎ እፎይታ
ከቀኝ ግድግዳየ ተጎራባች…. ሁሉ ባረፈበት ማታ
ዝምምምምምምታ !
ተኙ መሰል !!
* ** *
ሌላ ድምፅ ደግሞ ከግራ
በቆመ ጆሮየ ግርጌ ያልፋል ድሩን እያደራ
‹‹ እእእእእ ›› ይችኛይቱ ጎረቤቴ
እንዲህ በሙሉ ጨረቃ የሚያስቃዣት በሽተኛ
ሙሉ ሌሊት ስትዋትት ስትሰቃይ የማተኛ
ድፍን ሌሊት ስትዛብር ስታቃስት የሚነጋ
ሲጥ ሲጥጥ ወጉ እንዳይቀር የሷም አልጋ
ቀንም በመቀነቻ ነው … ወገቧን አስራ
የምትቆመው
የበሽታ ክፉ አካናድ ስጋዋን እየጎሰመው
በሁለት ቅስቻ መሃል … ግራ ቀኙኝ እያደመጥኩ
ካንዱ <ጆሮየ አውጭኝ> እያልኩ… ሌላውን
ባሳብ እያለምኩ
በመሃል የምኖር እኔ …
እንቅልፍ ሊጥለኝ ሲዳዳ በግዜር ላይ ቅኔ
እቀኛለሁ
የወጉን ፀሎት ሰም አድርጌ ‹‹በቀኝ አሳድረኝ
››እላለሁ
** **** ****
ኳኳኳኳኳኳኳኳኳኳ ኳ ኳ
አዲስ ተጋቢወች ማለዳ ተነስተው…. ለቁርስ
ቲማቲም እየቀጠቀጡ
ሲጥጥጥጥጥጥጥጥጥ
ታመው ያደሩቱ ቤተስኪያን ሊስሙ …..ከቤት
እየወጡ
በቀኝም በግራ እንዲህ የሚል ልሳን
‹‹ሰላም ያሳደርከን በሰላም አውለን ››
ይች ናት አገሬ … እኩል እግዚሃርን
የሚዘይሩባት… እኩል ያላደሩ
እኩል ቀን ጀማሪ እኩል ባልሆነ ቁርስ ተስፋ
እየቋጠሩ !
ከታች እስኪሾሙ ከላይ እስኪጠሩ !!
ከቀኝም ከግራም …መሃል ለሰፈሩ
ይች ናት አገሬ እንዲህ ነው አዳሩ !
🔘አሌክስ አብርሃም🔘
👍1
#ብቸኝነት_ማለት
ውዴ... ብቸኝነት...
ከሰዎች መነጠል...ለብቻ መቀመጥ...አይደለም ትርጉሙ፣
ጓደኛ አለመኖር...ብቻ ቀን ማሳለፍ...እሱ አይደል ህመሙ፣
ብቸኝነት ማለት...
ከሰው መንጋ ውሎ... ከሰው ተቀላቅሎ... ባዶነት መሰማት፣
የናፈቁትን ድምጽ... ከሩቅ እየሰሙ...በውስጥ ማዋራት፣
.
የናፈቁትን መልክ...ለብቻ እያለሙ...በናፍቆት መብከንከን፣
ቅርብ የሌለን ጠረን...ባፍንጫ እየማጉ...በሽታ'ው መታጠን፣
.
የድሮን ትዝታ ዛሬ እያሰቡ...፣
ከሃሳብ ማህደር ደግመው 'ያነበቡ...፣
.
በናፈቁት ሰው ድምጽ...የቅርቡን ሲጠሉ፣
የሚልቅን ጠረን...ካጠገብ አስቀምጠው...በሩቅ ሰው ሩሩሩሩሩቅ ጠረን...ባ'ሳብ ሲነጠሉ፣
.
ድሮ የሳቁትን...ደግምመው እያሰቡ...ሀዘን መሃል ሆነው...ለብቻ ሲፈግጉ፣
ድሮ ያዘኑበትን...ዛሬ እያስታወሱ...ከሞቀ ሳቅ መሃል...ለብቻ መንሰቅሰቅ...ማልቀስ ሲፈልጉ፣
.
ብቸኝነት ማለት...ትዝታ ማለት ነው...ማለት ነው ትዝታ፣
ከብዙ ሰው መሃል...ብ ቻ ነ ት መሰማት...ቀን የውሸት ስቀው...ብቻ ማልቀስ ማታ፣
.
ልክ እንዳሁናችን...ካጠገቤ 'ያለህ እንደምትናፍቀኝ...፣
ፍቅራችን አርጅቶ ምልክት በቀረው በትዝታ ሽበት... ዛሬ 'ንደሚታየኝ፣
.
ብቸኝነት ማለት የትዝታ ድርሳን...ነው የናፍቆት ክርታስ ...፣
ውዴ ፍቅሬ እያሉ በቋጠሩት ትላንት ዛሬን አንጀት ማራስ...፣
.
"እይዋት ስትናፍቀኝ ካጠገቤ አያለች" የሚል ዘፈን ማቆም
በመሃሙድ ዘፈን..."ምንድነው ትዝታ"... ከትካዜ መስጠም!
🔘የአብስራ ሞላ🔘
ውዴ... ብቸኝነት...
ከሰዎች መነጠል...ለብቻ መቀመጥ...አይደለም ትርጉሙ፣
ጓደኛ አለመኖር...ብቻ ቀን ማሳለፍ...እሱ አይደል ህመሙ፣
ብቸኝነት ማለት...
ከሰው መንጋ ውሎ... ከሰው ተቀላቅሎ... ባዶነት መሰማት፣
የናፈቁትን ድምጽ... ከሩቅ እየሰሙ...በውስጥ ማዋራት፣
.
የናፈቁትን መልክ...ለብቻ እያለሙ...በናፍቆት መብከንከን፣
ቅርብ የሌለን ጠረን...ባፍንጫ እየማጉ...በሽታ'ው መታጠን፣
.
የድሮን ትዝታ ዛሬ እያሰቡ...፣
ከሃሳብ ማህደር ደግመው 'ያነበቡ...፣
.
በናፈቁት ሰው ድምጽ...የቅርቡን ሲጠሉ፣
የሚልቅን ጠረን...ካጠገብ አስቀምጠው...በሩቅ ሰው ሩሩሩሩሩቅ ጠረን...ባ'ሳብ ሲነጠሉ፣
.
ድሮ የሳቁትን...ደግምመው እያሰቡ...ሀዘን መሃል ሆነው...ለብቻ ሲፈግጉ፣
ድሮ ያዘኑበትን...ዛሬ እያስታወሱ...ከሞቀ ሳቅ መሃል...ለብቻ መንሰቅሰቅ...ማልቀስ ሲፈልጉ፣
.
ብቸኝነት ማለት...ትዝታ ማለት ነው...ማለት ነው ትዝታ፣
ከብዙ ሰው መሃል...ብ ቻ ነ ት መሰማት...ቀን የውሸት ስቀው...ብቻ ማልቀስ ማታ፣
.
ልክ እንዳሁናችን...ካጠገቤ 'ያለህ እንደምትናፍቀኝ...፣
ፍቅራችን አርጅቶ ምልክት በቀረው በትዝታ ሽበት... ዛሬ 'ንደሚታየኝ፣
.
ብቸኝነት ማለት የትዝታ ድርሳን...ነው የናፍቆት ክርታስ ...፣
ውዴ ፍቅሬ እያሉ በቋጠሩት ትላንት ዛሬን አንጀት ማራስ...፣
.
"እይዋት ስትናፍቀኝ ካጠገቤ አያለች" የሚል ዘፈን ማቆም
በመሃሙድ ዘፈን..."ምንድነው ትዝታ"... ከትካዜ መስጠም!
🔘የአብስራ ሞላ🔘
👍6
#እንቧለሌ
ያረጀ ቂም ይዘን ፤ዘላለም ስንደግም፤
ዓለም ጥሎን ሄደ ፤እኛ ስናዘግም።
በወጣንበት በር ፣መልሰን ስንገባ፤
ስንት አደይ ረግፎ ፣ስንት ዘመን ጠባ።
ለኛ አልተሰጠም ወይ በይቅርታ መንፃት?
ስለ ፍቅር ሲባል ፣ያለፈን ቂም መርሳት።
መሪው ምረት የለሽ ፤ተመሪው ቅጥ ያጣ፤
በእንቧለሌ መንገድ ፣ማን አርነት ይውጣ ?።
እንዴው የሞኝ ዘፈን ሁል ጊዜ አበባዬ፤
ክፈል ትለኛለች ፤እኔን ያለዳዬ።
እንዴው ልክፈልስ ብል፣ በየትኛው ቁና ፣
መስፈሪያዋም ዐፈር ፣ሰፋሪው ጋር ሆና።
በመንታ ፊት ኑሮ ፣ቀን ይመላለሳል፤
እጅ እየሻከረ ፣እርፍ ይለሰልሳል።
በክንድ አዝል ሃገር ፣ሠው ከእንጨት ይረክሳል፤
እልፍ እየተለፋ ፣እፍኝ ይታፈሳል።
የትልቅ ፀብ ይሆን ፣ያማልዕክት እርግማን፣
መድረስ የተሳነን ፣እንዲህ ባገር አማን ።
ኧረ ምን መዓት ነው ? እንዴት ያል መለከፍ ?
ወንዙን ውሃ በላው ፤እኛ ስንጣለፍ ።
እንቧለሌ ስንዞር፣ ክቡን እንደምጣድ፤
ለእንጀራ እስከመቼ እሣት ላይ እንጣድ ።
ነቅቶ እየቀደመ ፣ኑሮን ካላደሰው ፣
ፀዳሉ ይረግፋል፤የቀንም እንደሰው።
🔘ኑረዲን ዒሣ🔘
ያረጀ ቂም ይዘን ፤ዘላለም ስንደግም፤
ዓለም ጥሎን ሄደ ፤እኛ ስናዘግም።
በወጣንበት በር ፣መልሰን ስንገባ፤
ስንት አደይ ረግፎ ፣ስንት ዘመን ጠባ።
ለኛ አልተሰጠም ወይ በይቅርታ መንፃት?
ስለ ፍቅር ሲባል ፣ያለፈን ቂም መርሳት።
መሪው ምረት የለሽ ፤ተመሪው ቅጥ ያጣ፤
በእንቧለሌ መንገድ ፣ማን አርነት ይውጣ ?።
እንዴው የሞኝ ዘፈን ሁል ጊዜ አበባዬ፤
ክፈል ትለኛለች ፤እኔን ያለዳዬ።
እንዴው ልክፈልስ ብል፣ በየትኛው ቁና ፣
መስፈሪያዋም ዐፈር ፣ሰፋሪው ጋር ሆና።
በመንታ ፊት ኑሮ ፣ቀን ይመላለሳል፤
እጅ እየሻከረ ፣እርፍ ይለሰልሳል።
በክንድ አዝል ሃገር ፣ሠው ከእንጨት ይረክሳል፤
እልፍ እየተለፋ ፣እፍኝ ይታፈሳል።
የትልቅ ፀብ ይሆን ፣ያማልዕክት እርግማን፣
መድረስ የተሳነን ፣እንዲህ ባገር አማን ።
ኧረ ምን መዓት ነው ? እንዴት ያል መለከፍ ?
ወንዙን ውሃ በላው ፤እኛ ስንጣለፍ ።
እንቧለሌ ስንዞር፣ ክቡን እንደምጣድ፤
ለእንጀራ እስከመቼ እሣት ላይ እንጣድ ።
ነቅቶ እየቀደመ ፣ኑሮን ካላደሰው ፣
ፀዳሉ ይረግፋል፤የቀንም እንደሰው።
🔘ኑረዲን ዒሣ🔘
#ህመሜን_ፍለጋ
ትኩሳት ነው ብለው
ሰዎች ይነግሩኛል፣
ራስ ምታት ነው ብለው
ይገምቱልኛል፣
:
ግማሹ እየመጣ
ጨጓራ ይዞሃል
ብሎ እየነገረኝ፤
ግማሹ ሰው ደግሞ
ኩላሊት አለብህ
ብሎ እየነገረኝ፤
ህመሜን ሰው ሁሉ
ስም እያወጣለት፤
ለየትኛው ህመም ክኒን ልዋጥለት፤
ለየትኛው ህመም መርፌ ልወጋለት።
:
የቱ ነው ህመሜ?
እንደምን ልወቀው?፣
ወይ ህመም አይዋጥ
ህመም በሽታዬን እንዴት ልደብቀው?፣
:
ቸገረኝ!
:
ብቻ!
የበሽታዬን ስም
ንገሩኝ ልለየው፤
ፍለጋው ነው እንጂ
ህመም ስቃዩ አይደል
ነፍሴን የሚለየው፤
:
ሞትማ ክብር ነው
ሞትማ 'ረፍት ነው
ቅር ቢሉት የማይቀር፤
ከነጥያቄዬ ወደ ሌላኛ ዓለም
መሄድ መጓዜ ግን
ሰላም እንዳይነሳኝ
ከነፍሴ ጋር ሄዶ እንዳይሰነቀር።
:
ግድ የለም ንገሩኝ
ህመሜ ምንድነው?
:
ጠሃይዋን እያየው ብርድ ብርድ የሚለኝ
በረዶ እየጣለ ሙቀት የሚገለኝ
ከቶ ምን ሆኜ ነው?
:
ወባ ነው እንዳልል
አጎበር ዘርግቼ፤
ብርድ ነው እንዳልል
ልብስ ደራርቤ
እሳትም አንድጄ ቤቴንም ዘግቼ፤
:
ለምን ይበርደኛል?
:
ለምን ይሞቀኛል?
:
እጅ እግሬ ጉልበቴስ
ምን ሆንኩኝ ብሎ ነው
'ሚቆረጣጥመኝ?
ምን ሆንኩኝ ብዬ ነው
ስኳር የሚመረኝ እሬት የሚጥመኝ?
:
ምን እንደሆንኩ እንጃ!
:
ህመሜን መለየት
ማወቁን አላውቀው፤
እንዳው ዝም ብዬ ነው
ቁስሌን እያየሁ
ትናንት ዛሬም ነገም
ሁሌም ምጠይቀው፤
:
ኬት መጣ ይህ ቁስል?
የት ነው የተጋጋጥሁ?
ወዴት ልዘል ይሆን
እግሬን ተሰብሬ
የስቃይ ምጥ ያማጥሁ
:
እንዳው ላመል እንጂ!
:
እንደታመምኩኝስ
እንዳልታመምኩኝስ
ከወዴት አውቄው፤
እንዳው ላመል እንጂ
ጠይቅ ስለተባልኩ
እንዲህ ምጠይቀው፤
:
እንደዚህ እያልኩኝ!
:
ህመሜን ሰው ሁሉ
ስም እያወጣለት፤
ለየትኛው ህመም ክኒን ልዋጥለት፤
ለየትኛው ህመም መርፌ ልወጋለት።
እንጃ!
ትኩሳት ነው ብለው
ሰዎች ይነግሩኛል፣
ራስ ምታት ነው ብለው
ይገምቱልኛል፣
:
ግማሹ እየመጣ
ጨጓራ ይዞሃል
ብሎ እየነገረኝ፤
ግማሹ ሰው ደግሞ
ኩላሊት አለብህ
ብሎ እየነገረኝ፤
ህመሜን ሰው ሁሉ
ስም እያወጣለት፤
ለየትኛው ህመም ክኒን ልዋጥለት፤
ለየትኛው ህመም መርፌ ልወጋለት።
:
የቱ ነው ህመሜ?
እንደምን ልወቀው?፣
ወይ ህመም አይዋጥ
ህመም በሽታዬን እንዴት ልደብቀው?፣
:
ቸገረኝ!
:
ብቻ!
የበሽታዬን ስም
ንገሩኝ ልለየው፤
ፍለጋው ነው እንጂ
ህመም ስቃዩ አይደል
ነፍሴን የሚለየው፤
:
ሞትማ ክብር ነው
ሞትማ 'ረፍት ነው
ቅር ቢሉት የማይቀር፤
ከነጥያቄዬ ወደ ሌላኛ ዓለም
መሄድ መጓዜ ግን
ሰላም እንዳይነሳኝ
ከነፍሴ ጋር ሄዶ እንዳይሰነቀር።
:
ግድ የለም ንገሩኝ
ህመሜ ምንድነው?
:
ጠሃይዋን እያየው ብርድ ብርድ የሚለኝ
በረዶ እየጣለ ሙቀት የሚገለኝ
ከቶ ምን ሆኜ ነው?
:
ወባ ነው እንዳልል
አጎበር ዘርግቼ፤
ብርድ ነው እንዳልል
ልብስ ደራርቤ
እሳትም አንድጄ ቤቴንም ዘግቼ፤
:
ለምን ይበርደኛል?
:
ለምን ይሞቀኛል?
:
እጅ እግሬ ጉልበቴስ
ምን ሆንኩኝ ብሎ ነው
'ሚቆረጣጥመኝ?
ምን ሆንኩኝ ብዬ ነው
ስኳር የሚመረኝ እሬት የሚጥመኝ?
:
ምን እንደሆንኩ እንጃ!
:
ህመሜን መለየት
ማወቁን አላውቀው፤
እንዳው ዝም ብዬ ነው
ቁስሌን እያየሁ
ትናንት ዛሬም ነገም
ሁሌም ምጠይቀው፤
:
ኬት መጣ ይህ ቁስል?
የት ነው የተጋጋጥሁ?
ወዴት ልዘል ይሆን
እግሬን ተሰብሬ
የስቃይ ምጥ ያማጥሁ
:
እንዳው ላመል እንጂ!
:
እንደታመምኩኝስ
እንዳልታመምኩኝስ
ከወዴት አውቄው፤
እንዳው ላመል እንጂ
ጠይቅ ስለተባልኩ
እንዲህ ምጠይቀው፤
:
እንደዚህ እያልኩኝ!
:
ህመሜን ሰው ሁሉ
ስም እያወጣለት፤
ለየትኛው ህመም ክኒን ልዋጥለት፤
ለየትኛው ህመም መርፌ ልወጋለት።
እንጃ!
👍2
#የመልስ_ጉዞ…
:
ክፍል- #አንድ
✍
:
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
ፍእማዊ መንግስታዊ አስተዳደር ፤ፍፁማዊ ማህበረሳብ አወቀቀር፤ፍፁማዊ የተፈጥሮ ሚዛኗን የጠበቀች ሀገር..በዩቶፕያ ፅንሰ ሀሳብ የታነፀች ማለት ያቺ ነች ፡፡በነብያት አዕምሮ ውሰጥ ከዘመናት በፊት ተፀንሳ ትንቢት የተነገረላት ሰማያዊ የመኖሪያ ስፍራ በነአፍላጦስ ምናብ የተፀነሰችና በምድር ለመገንባት የተመኙላት ምድራዊ እንከን አልባ የሰለጠኑና የበቁ ማህበረሰቦች የሚኖሩባት ፤በፍፅም ፍትሀዊነት እና በጋራ ህግ የሚመራ መንግስት ያላት፤ ለገነት የቀረበ ልምላሜ ኖሯት አንድ ቀን በጋራ ስምምነት ፍፅማዊ ደስታ የምታመነጭ ተደርጋ የምትመሰረት ምድራዊ ከተማ ….
ታዲያ ይህቺ የአለማዊው እሳቤ እና የመንፈሳዊው ትንቢት ቀላቅላ የያዘች ዩቶፐያ ከወዴት ነች?የሀይማኖት ነብያት እንደሚሉት በሰማይ ከሞት ቡኃላ ባለው ህይወት የሚያገኞት ወይስ ሰው የልዕለ ሰብነትን ዙፋን ሲቆናጠጥ ፍፁም ፍትሀዊ፤ ፍፁም ዘመናዊ ብቃት ባገኘ ጊዜ በብቃትና በጥበቡ እዚሁ ምድር ላይ የሚመሰርታት….?
ወደ ዩቶፕያ መሄጂያ መንገዱ በየት ነው…ዩቶፕያስ የት ነው እውን ሊሆን የሚችለው ….?
እግዚያብሄር መላክ በምስራቅ በኤደን የአትክልት ስፍራ አዘጋጀ ያበጀውንም ሰው በዛ አኖረው፡፡እግዚያሄር አምላክ ለዓይን የሚያስደስት ለመብልም መልካም የሆነውን ዛፍ ሁሉ በምድር አበቀለ፡፡ በአትክልቱ ቦታ መልካም የህይወት ዛፍ ነበር፡፡እንዲሁም መልካምና ክፍውን መለየት ሚያስችል የዕውቀት ዛፍም ነበር፡፡የአትክልት ስፋራ የሚያጠጣው ወንዝ ከዔደን ይፈስ ነበር ፡፡ከዚያም በአራት ተከፍሎ ይፈስ ነበር፡፡የመጀመሪያው በምድሩ ወርቅ የሚገኝበት በሐዊላ ምድር ዙሪያ ሁሉ የሚፈሰው የፊሶን ወንዝ ነው፡፡ኤውላጥ ምርጥ ሆነ ወርቅ መልካም መአዛ ያለው ከርቤና የከበረ ድንጋይ የሚገኝበት ምደር ነው፡፡ሁለተኛው በኢትዬጳያ ምድር ዙሪያ ሁሉ የሚፈስው ግዬን ወንዝ ነው፡፡ሶስተኛው ከአሶር በስተምስራቅ ሚፈሰው የጤግሮስ ወንዝ ሲሆን አራተኛው የኤፍራጠስ ወንዝ ነው፡፡ (ዘፍጥረት ም 2 ቁጥር 8-14 )
ለመሆኑ ይሄስ ስፍራ የት ነው?፡፡የአዳምና ሄዋን ቀደምት መኖሪያ ስፍራ ..?የእውቀትና የዘላለም ፍሬ የሚበቅልበት ሚስጥራዊ ስፍራ…?በአዳምና ሄዋና የተወከሉት የመጀመሪያዎቹ የሰው ልጆች በፈጣሪያቸው ላይ ከብልሁ እባብ ጋር የመከሩበት ፤የመከሩበት ብቻ ሳይሆን የዶለቱበትም ስፍራ የት ነው?፡ከዛስ እርቃናቸውን እንደሆኑ የተገለፀላቸው…?ያን ሰፊ እፍረታቸውን የጋረዱበት ቅጠልስ ከየትኛው ስፍራ ከየትኛውስ ዛፍ ላይስ የተገንጥለው ይሆን? …ከዛስ ወደየት ተባረሩ ?እንዚህ መሰረታዊ ጥያቄዎች ናቸው፡፡የመልስ ጉዞው ወደዛ ነዋ ፡፡አያቶቾ አዳምና ሄዋን ወደተባሩበት ስፍራ ወደ ሀገረ ገነት ...
ይህቺ ሀገር ኢትዬጵያ ነች፤ ይህቺ ሀገር የአያቴ ህልም ነች…ህልሙ ግን በከፊል እንኳን እውን ሳይሆን እድሜ እየተጫጫነው ነው፡፡ቢሆንም ለዚህ አንድ ዘዴ ዘይዷል …ህልሙ ህልሜ እንዲሆን አድርጎል…እንደሱ እንድመኝ ….እንደእሱ እንዳስብ…. ግን ይሄን ህልም እውን ለማድረግ እኔ ምን ማድረግ አለብኝ…ከሚስቴ ጋ እስክገናኝ ምንም የማውቀው ነገር አልነበረም..
አሁን ግን ወደ እዛች ስፍራ ጉዞ ጀምረናል ፡፡እኔና ሚስቴ ፡፡ሁለታችንም የተለያየ የግል ዓላማ አለን ፡፡ግን የየግል አላማችን ከተሳካን ቡኃላም የጋራም አንድ አላማ አለን፡፡ አዎ እንብርት የሆነውን ስፍራ ካገኘን ቡኃላ ዩቶፐያችንን በስፍራው ደግመን እንገነባለን..እንዴት አድርገን.? ወደፊት አብረን የምናየው ይሆናል፡፡
አሁን ወደዋናው የታሪኩ ክፍል ጠልቄ ከመግባቴ በፊት እራሴን ላስተዋውቃችሁ …መቼስ ታሪኬን ስትሰሙ አንዳንዶቻችሁ የተዛባ አዕምሮ የፈጠራቸው የእድሜ ልክ የቀን ቅዥቶች ልትሉት እንድምትችሉ እገምታለው፡፡ይሁንና የእኔን እውነት ነግራችሆለው፡፡ ሳልኩልና ሳልቀባባ ጥሬ እወነቱን ብቻ፡፡ማመን ያለማመን የእናንተ ፋንታ ነው፡፡ግን ከእኔ ጋር ወዳጅነት መስርታችሁ የምነግራችሁን ለማድመጥ በጣም ትዕግስተኛ እና አስተዋይ መሆን አለባችሁ፡፡ምክንያቱም የሆነ ርዕስ ተከትሎ የነገሮችን ቅደም ተከለተልን ጠብቆ ታሪኩን ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው ያጫውተናል ብላቹ ምትጠብቁ ከሆነ ከአሁኑ እርማችሁን አውጡ ፡፡እና ንባባችሁን እዚህ ጋር አቋርጡ፡፡
የገዛ የራሴን ታሪክ ለሌላ ሰው እንዴት ማውጋት እንዳለብኝ መወሰን ስልጣን ያለኝ እኔ ብቻ ነኝ ፡፡ስለዚህ ዘባራቂነቴን ካልወደዳችሁት ምንም ልረዳችሁ አልችልም፡፡ዘባራቂነቴ የነፃነቴ መገለጫ ምልክት ነው፡፡ምናቤ በማንኛውም የስርዓትና የደንብ ሰንሰለት አለመጠፍነጉን የሚያሳይ ልቅ መጋለቢያ ሜዳ አይነት ነው፡፡ወይንም በሆነ ቦታ የታጠረ የኩሬ ውሀ ሳይሆን የአባይ አይነት ሀገር ተሸጋሪ ወንዝ ፡፡አዎ የእኔ አዕምሮ እንደዛ ነው፡፡ለነፍሴ ማደሪያ በተሰጠኝ አካል ያልተወሰነ እንዳምንበት ከቤተሰቤ በውርስ በተሰጠኝ ሀይማኖታዊ ዶግማ ያልታጠረ.. በተወለድኩበት ሀገር ድንበር ያልተከለለ….በተፈጠርኩበት ምድር የልተገደበ…እንደዛ ነው ምናቤ… እንደዛው ነው ሀሳቤ …..
እና ታዲያ እንዴት ሆኖ ነው ካልከኝ በዘመን ሂደት ሰው ያው ሰው ነውና መጎዝና አዲስ ነገር ማሰስ ተፈጥሮአዊው ባህሪው እንደመሆኑ መጠን አካባቢውን እየለቀቀ ሲያፈገፍግ ሲዋለድ ሲራባ ሲያፈገፍግ በሚሊዬን ዓመት ሂደት ውስጥ መቶች ውስጥ አለመን አዳረሰና በዚህ ሂደት ውስት ከተፈጥሮ እና እርስበርሱ በሚያደርገው ትግልና ፍትጊያ አእምሮውን እያዳበረ አዕምሮ ሲዳብር ደግሞ ለአካባቢውም ሆነ ለራሱ የነበረው እይታ እየተቀየረ የማምረቻ መሰሪያዎችን እየፈለሰፈ ንግድና እየጀመረ ሲመጣ መልሶ ወደ መነሻው ማየት ጀመረ…ኢትዬጵያ የሰው ዘር ተፈጥሮ የተበተነባት ምድር መልሶም አንድ ቀን የሚሰበሰብባት፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
ክፍል- #አንድ
✍
:
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
ፍእማዊ መንግስታዊ አስተዳደር ፤ፍፁማዊ ማህበረሳብ አወቀቀር፤ፍፁማዊ የተፈጥሮ ሚዛኗን የጠበቀች ሀገር..በዩቶፕያ ፅንሰ ሀሳብ የታነፀች ማለት ያቺ ነች ፡፡በነብያት አዕምሮ ውሰጥ ከዘመናት በፊት ተፀንሳ ትንቢት የተነገረላት ሰማያዊ የመኖሪያ ስፍራ በነአፍላጦስ ምናብ የተፀነሰችና በምድር ለመገንባት የተመኙላት ምድራዊ እንከን አልባ የሰለጠኑና የበቁ ማህበረሰቦች የሚኖሩባት ፤በፍፅም ፍትሀዊነት እና በጋራ ህግ የሚመራ መንግስት ያላት፤ ለገነት የቀረበ ልምላሜ ኖሯት አንድ ቀን በጋራ ስምምነት ፍፅማዊ ደስታ የምታመነጭ ተደርጋ የምትመሰረት ምድራዊ ከተማ ….
ታዲያ ይህቺ የአለማዊው እሳቤ እና የመንፈሳዊው ትንቢት ቀላቅላ የያዘች ዩቶፐያ ከወዴት ነች?የሀይማኖት ነብያት እንደሚሉት በሰማይ ከሞት ቡኃላ ባለው ህይወት የሚያገኞት ወይስ ሰው የልዕለ ሰብነትን ዙፋን ሲቆናጠጥ ፍፁም ፍትሀዊ፤ ፍፁም ዘመናዊ ብቃት ባገኘ ጊዜ በብቃትና በጥበቡ እዚሁ ምድር ላይ የሚመሰርታት….?
ወደ ዩቶፕያ መሄጂያ መንገዱ በየት ነው…ዩቶፕያስ የት ነው እውን ሊሆን የሚችለው ….?
እግዚያብሄር መላክ በምስራቅ በኤደን የአትክልት ስፍራ አዘጋጀ ያበጀውንም ሰው በዛ አኖረው፡፡እግዚያሄር አምላክ ለዓይን የሚያስደስት ለመብልም መልካም የሆነውን ዛፍ ሁሉ በምድር አበቀለ፡፡ በአትክልቱ ቦታ መልካም የህይወት ዛፍ ነበር፡፡እንዲሁም መልካምና ክፍውን መለየት ሚያስችል የዕውቀት ዛፍም ነበር፡፡የአትክልት ስፋራ የሚያጠጣው ወንዝ ከዔደን ይፈስ ነበር ፡፡ከዚያም በአራት ተከፍሎ ይፈስ ነበር፡፡የመጀመሪያው በምድሩ ወርቅ የሚገኝበት በሐዊላ ምድር ዙሪያ ሁሉ የሚፈሰው የፊሶን ወንዝ ነው፡፡ኤውላጥ ምርጥ ሆነ ወርቅ መልካም መአዛ ያለው ከርቤና የከበረ ድንጋይ የሚገኝበት ምደር ነው፡፡ሁለተኛው በኢትዬጳያ ምድር ዙሪያ ሁሉ የሚፈስው ግዬን ወንዝ ነው፡፡ሶስተኛው ከአሶር በስተምስራቅ ሚፈሰው የጤግሮስ ወንዝ ሲሆን አራተኛው የኤፍራጠስ ወንዝ ነው፡፡ (ዘፍጥረት ም 2 ቁጥር 8-14 )
ለመሆኑ ይሄስ ስፍራ የት ነው?፡፡የአዳምና ሄዋን ቀደምት መኖሪያ ስፍራ ..?የእውቀትና የዘላለም ፍሬ የሚበቅልበት ሚስጥራዊ ስፍራ…?በአዳምና ሄዋና የተወከሉት የመጀመሪያዎቹ የሰው ልጆች በፈጣሪያቸው ላይ ከብልሁ እባብ ጋር የመከሩበት ፤የመከሩበት ብቻ ሳይሆን የዶለቱበትም ስፍራ የት ነው?፡ከዛስ እርቃናቸውን እንደሆኑ የተገለፀላቸው…?ያን ሰፊ እፍረታቸውን የጋረዱበት ቅጠልስ ከየትኛው ስፍራ ከየትኛውስ ዛፍ ላይስ የተገንጥለው ይሆን? …ከዛስ ወደየት ተባረሩ ?እንዚህ መሰረታዊ ጥያቄዎች ናቸው፡፡የመልስ ጉዞው ወደዛ ነዋ ፡፡አያቶቾ አዳምና ሄዋን ወደተባሩበት ስፍራ ወደ ሀገረ ገነት ...
ይህቺ ሀገር ኢትዬጵያ ነች፤ ይህቺ ሀገር የአያቴ ህልም ነች…ህልሙ ግን በከፊል እንኳን እውን ሳይሆን እድሜ እየተጫጫነው ነው፡፡ቢሆንም ለዚህ አንድ ዘዴ ዘይዷል …ህልሙ ህልሜ እንዲሆን አድርጎል…እንደሱ እንድመኝ ….እንደእሱ እንዳስብ…. ግን ይሄን ህልም እውን ለማድረግ እኔ ምን ማድረግ አለብኝ…ከሚስቴ ጋ እስክገናኝ ምንም የማውቀው ነገር አልነበረም..
አሁን ግን ወደ እዛች ስፍራ ጉዞ ጀምረናል ፡፡እኔና ሚስቴ ፡፡ሁለታችንም የተለያየ የግል ዓላማ አለን ፡፡ግን የየግል አላማችን ከተሳካን ቡኃላም የጋራም አንድ አላማ አለን፡፡ አዎ እንብርት የሆነውን ስፍራ ካገኘን ቡኃላ ዩቶፐያችንን በስፍራው ደግመን እንገነባለን..እንዴት አድርገን.? ወደፊት አብረን የምናየው ይሆናል፡፡
አሁን ወደዋናው የታሪኩ ክፍል ጠልቄ ከመግባቴ በፊት እራሴን ላስተዋውቃችሁ …መቼስ ታሪኬን ስትሰሙ አንዳንዶቻችሁ የተዛባ አዕምሮ የፈጠራቸው የእድሜ ልክ የቀን ቅዥቶች ልትሉት እንድምትችሉ እገምታለው፡፡ይሁንና የእኔን እውነት ነግራችሆለው፡፡ ሳልኩልና ሳልቀባባ ጥሬ እወነቱን ብቻ፡፡ማመን ያለማመን የእናንተ ፋንታ ነው፡፡ግን ከእኔ ጋር ወዳጅነት መስርታችሁ የምነግራችሁን ለማድመጥ በጣም ትዕግስተኛ እና አስተዋይ መሆን አለባችሁ፡፡ምክንያቱም የሆነ ርዕስ ተከትሎ የነገሮችን ቅደም ተከለተልን ጠብቆ ታሪኩን ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው ያጫውተናል ብላቹ ምትጠብቁ ከሆነ ከአሁኑ እርማችሁን አውጡ ፡፡እና ንባባችሁን እዚህ ጋር አቋርጡ፡፡
የገዛ የራሴን ታሪክ ለሌላ ሰው እንዴት ማውጋት እንዳለብኝ መወሰን ስልጣን ያለኝ እኔ ብቻ ነኝ ፡፡ስለዚህ ዘባራቂነቴን ካልወደዳችሁት ምንም ልረዳችሁ አልችልም፡፡ዘባራቂነቴ የነፃነቴ መገለጫ ምልክት ነው፡፡ምናቤ በማንኛውም የስርዓትና የደንብ ሰንሰለት አለመጠፍነጉን የሚያሳይ ልቅ መጋለቢያ ሜዳ አይነት ነው፡፡ወይንም በሆነ ቦታ የታጠረ የኩሬ ውሀ ሳይሆን የአባይ አይነት ሀገር ተሸጋሪ ወንዝ ፡፡አዎ የእኔ አዕምሮ እንደዛ ነው፡፡ለነፍሴ ማደሪያ በተሰጠኝ አካል ያልተወሰነ እንዳምንበት ከቤተሰቤ በውርስ በተሰጠኝ ሀይማኖታዊ ዶግማ ያልታጠረ.. በተወለድኩበት ሀገር ድንበር ያልተከለለ….በተፈጠርኩበት ምድር የልተገደበ…እንደዛ ነው ምናቤ… እንደዛው ነው ሀሳቤ …..
እና ታዲያ እንዴት ሆኖ ነው ካልከኝ በዘመን ሂደት ሰው ያው ሰው ነውና መጎዝና አዲስ ነገር ማሰስ ተፈጥሮአዊው ባህሪው እንደመሆኑ መጠን አካባቢውን እየለቀቀ ሲያፈገፍግ ሲዋለድ ሲራባ ሲያፈገፍግ በሚሊዬን ዓመት ሂደት ውስጥ መቶች ውስጥ አለመን አዳረሰና በዚህ ሂደት ውስት ከተፈጥሮ እና እርስበርሱ በሚያደርገው ትግልና ፍትጊያ አእምሮውን እያዳበረ አዕምሮ ሲዳብር ደግሞ ለአካባቢውም ሆነ ለራሱ የነበረው እይታ እየተቀየረ የማምረቻ መሰሪያዎችን እየፈለሰፈ ንግድና እየጀመረ ሲመጣ መልሶ ወደ መነሻው ማየት ጀመረ…ኢትዬጵያ የሰው ዘር ተፈጥሮ የተበተነባት ምድር መልሶም አንድ ቀን የሚሰበሰብባት፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍5
#ፈጣሪ_ብሔሩ_ምንድን_ነው... ?
ህመሜን ፍለጋ
ትኩሳት ነው ብለው
ሰዎች ይነግሩኛል፣
ራስ ምታት ነው ብለው
ይገምቱልኛል፣
:
ግማሹ እየመጣ
ጨጓራ ይዞሃል
ብሎ እየነገረኝ፤
ግማሹ ሰው ደግሞ
ኩላሊት አለብህ
ብሎ እየነገረኝ፤
ህመሜን ሰው ሁሉ
ስም እያወጣለት፤
ለየትኛው ህመም ክኒን ልዋጥለት፤
ለየትኛው ህመም መርፌ ልወጋለት።
:
ብቻ ይሄው ምልክቱ፣
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን ደፍሬ
እንዲህ ያስብለኛል፤
ለንፁሀኑ በደል
ለንፁሀኑ ደም ወርደህ እንድትፈርድ
በምነኛ እንፁም በምነኛ እንስገድ፤
በትግርኛ እንስገድ?
በአማርኛ እንስገድ?
በኦሮምኛ እንስገድ?
የቱ ነው ሚቀርብህ
የትኛው ነው ያንተ ብሔር ያሰኘኛል፤
ስሙ ጠፋኝ እንጂ እውነት ነው አሞኛል፤
:
ግን ግን ይህ ህመም ምንድን ነው?
እንደምን ልወቀው?
ህመሜን እንዳልውጥ
ስቃዩ በዛብኝ እንዴት ልደብቀው፤
:
ቸገረኝ!
:
እስኪ ታውቁ እንደሆን
የበሽታዬን ስም
ንገሩኝ ልለየው፤
ፍለጋው ነው እንጂ
ህመም ስቃዩ አይደል
ነፍሴን የሚለየው፤
:
ብቻ ይሄው ምልክቱ
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን
ደፍሬ እንዲህ ያስብለኛል፤
ጥበብ ያልከኝን ቃል
በቃሌ መዝገብ ላይ እየተረጎምኩኝ
ጠብቤ ጠብቤ ጎሳህን ዘረክን ብሄርክን ጠየኩኝ
ጌታ ግን ምንድን ነህ ?
ኦሮሞ
ጉራጌ
ሱማሌ
ሀረርጌ
ትግሬ ነህ አማራ፤
ቤተስኪያን አልሄድም
መስጊድም አልሄድም ዘርክን እስካጣራ
ማለትም ያምረኛል
ስሙ ጠፋኝ እንጂ እውነት ነው አሞኛል፤
ግን ግን ይህ ህመም ምንድን ነው?
እንደምን ልወቀው?
ህመሜን እንዳልውጥ
ስቃዩ በዛብኝ እንዴት ልደብቀው፤
:
ሞትማ ክብር ነው
ሞትማ 'ረፍት ነው
ቅር ቢሉት የማይቀር፤
ከነጥያቄዬ ወደ ሌላኛው ዓለም
መሄድ መጓዜ ግን
ሰላም እንዳይነሳኝ
ከነፍሴ ጋር ሄዶ እንዳይሰነቀር።
:
ብቻ ይሄው ምልክቱ
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን
ደፍሬ እንዲህ ያስብለኛል፤
:
በፈጠርካት ምድር ድንበር አበጅተን
የኔ ነው የኔ ነው ተባብለን አድረናል
ሁሉ ያንተ መሆኑን ዘንግተን ከኖርን
ብዙ አመት ሆኖናል፤
:
ይሄው ስማኝማ በባቢሎን
ምክንያት ሀጥያታችን በዝቶ፤
:
ቋንቋ ልሳናችን ለይተህ ቃኝተካል
ግድ የለም አሁን ግን ቋንቋችንን ቀማን
እንዳደርስብህ ግንቡ ይሻልካል፤
:
ይሄው ስማኝማ አንተን ልናከብር
የፈጠርክልን አንደበት ተዘጋ፤
:
አንተን ዘንግተናል ውዳሲያችን ሁሉ
ዘሬ ዘሬ ሆኖል በነጋ በጠባ
:
ግን ግን ይህ ህመም ምንድን ነው?
እንደምን ልወቀው?
ህመሜን እንዳልውጥ
ስቃዩ በዛብኝ እንዴት ልደብቀው
:
:
ግድ የለም ንገሩኝ
ህመሜ ምንድነው?
:
ጠሃይዋን እያየው ብርድ ብርድ የሚለኝ
በረዶ እየጣለ ሙቀት የሚገለኝ
ከቶ ምን ሆኜ ነው?
:
ወባ ነው እንዳልል
አጎበር ዘርግቼ፤
ብርድ ነው እንዳልል
ልብስ ደራርቤ
እሳትም አንድጄ ቤቴንም ዘግቼ፤
:
ለምን ይበርደኛል?
:
ለምን ይሞቀኛል?
:
እጅ እግሬ ጉልበቴስ
ምን ሆንኩኝ ብሎ ነው
'ሚቆረጣጥመኝ?
ምን ሆንኩኝ ብዬ ነው
ስኳር የሚመረኝ እሬት የሚጥመኝ?
:
ምን እንደሆንኩ እንጃ
:
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን ደፍሬ
እንዲህ ያስብለኛል፤
:
በልሙጥ ሰማይ ላይ ሰንደቄን ስላየው
ኮከቡን አጥፋልኝ ብዬ እጠይቃለው
ስሙን ባላውቀውም እውነት ታምሚያለው፤
:
ካስርቱ ትዛዛት አንድ የጨመርክበት
አልያም ያጎደልከው ሆኖ እየተሰማኝ
ህግ ሻርክ ብዬ መበታተን ጠማኝ፤
እንዲህም አስባለው
ስሙን ባላውቀውም እውነት ታምሜአለሁ
፡
ምን እንደሆንኩ እንጃ!
:
ህመሜን መለየት
ማወቁን አላውቀው፤
እንዳው ዝም ብዬ ነው
ቁስሌን እያየሁ
ትናንት ዛሬም ነገም
ሁሌም ምጠይቀው፤
:
ኬት መጣ ይህ ቁስል?
የት ነው የተጋጋጥሁ?
ወዴት ልዘል ይሆን
እግሬን ተሰብሬ
የስቃይ ምጥ ያማጥሁ
:
ምን እንደሆንኩ እንጃ!
:
እየጠዘጠዘኝ
እየቀዘቀዘኝ
እየገዘገዘኝ
:
የኔ ሰው እርቆኝ
ነው ጠላት የገነዘኝ፤
እያልኩ አስባለው
:
ከወዳጄም ጥል ነኝ
ከጠሌቴም ጥል ነኝ
ከራሴም ጋር ጥል ነኝ
:
እውነት ታምሜአለሁ
:
እንዲያው ዝም ብዬ እንጂ
:
እንደታመምኩኝስ
እንዳልታመምኩኝስ
ከወዴት አውቄው፤
እንዳው ላመል እንጂ
ጠይቅ ስለተባልኩ
እንዲህ ምጠይቀው፤
:
እንደዚህ እያልኩኝ!
:
ህመሜን ሰው ሁሉ
ስም እያወጣለት፤
ለየትኛው ህመም ክኒን ልዋጥለት፤
ለየትኛው ህመም መርፌ ልወጋለት።
እንጃ!
ህመሜን ፍለጋ
ትኩሳት ነው ብለው
ሰዎች ይነግሩኛል፣
ራስ ምታት ነው ብለው
ይገምቱልኛል፣
:
ግማሹ እየመጣ
ጨጓራ ይዞሃል
ብሎ እየነገረኝ፤
ግማሹ ሰው ደግሞ
ኩላሊት አለብህ
ብሎ እየነገረኝ፤
ህመሜን ሰው ሁሉ
ስም እያወጣለት፤
ለየትኛው ህመም ክኒን ልዋጥለት፤
ለየትኛው ህመም መርፌ ልወጋለት።
:
ብቻ ይሄው ምልክቱ፣
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን ደፍሬ
እንዲህ ያስብለኛል፤
ለንፁሀኑ በደል
ለንፁሀኑ ደም ወርደህ እንድትፈርድ
በምነኛ እንፁም በምነኛ እንስገድ፤
በትግርኛ እንስገድ?
በአማርኛ እንስገድ?
በኦሮምኛ እንስገድ?
የቱ ነው ሚቀርብህ
የትኛው ነው ያንተ ብሔር ያሰኘኛል፤
ስሙ ጠፋኝ እንጂ እውነት ነው አሞኛል፤
:
ግን ግን ይህ ህመም ምንድን ነው?
እንደምን ልወቀው?
ህመሜን እንዳልውጥ
ስቃዩ በዛብኝ እንዴት ልደብቀው፤
:
ቸገረኝ!
:
እስኪ ታውቁ እንደሆን
የበሽታዬን ስም
ንገሩኝ ልለየው፤
ፍለጋው ነው እንጂ
ህመም ስቃዩ አይደል
ነፍሴን የሚለየው፤
:
ብቻ ይሄው ምልክቱ
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን
ደፍሬ እንዲህ ያስብለኛል፤
ጥበብ ያልከኝን ቃል
በቃሌ መዝገብ ላይ እየተረጎምኩኝ
ጠብቤ ጠብቤ ጎሳህን ዘረክን ብሄርክን ጠየኩኝ
ጌታ ግን ምንድን ነህ ?
ኦሮሞ
ጉራጌ
ሱማሌ
ሀረርጌ
ትግሬ ነህ አማራ፤
ቤተስኪያን አልሄድም
መስጊድም አልሄድም ዘርክን እስካጣራ
ማለትም ያምረኛል
ስሙ ጠፋኝ እንጂ እውነት ነው አሞኛል፤
ግን ግን ይህ ህመም ምንድን ነው?
እንደምን ልወቀው?
ህመሜን እንዳልውጥ
ስቃዩ በዛብኝ እንዴት ልደብቀው፤
:
ሞትማ ክብር ነው
ሞትማ 'ረፍት ነው
ቅር ቢሉት የማይቀር፤
ከነጥያቄዬ ወደ ሌላኛው ዓለም
መሄድ መጓዜ ግን
ሰላም እንዳይነሳኝ
ከነፍሴ ጋር ሄዶ እንዳይሰነቀር።
:
ብቻ ይሄው ምልክቱ
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን
ደፍሬ እንዲህ ያስብለኛል፤
:
በፈጠርካት ምድር ድንበር አበጅተን
የኔ ነው የኔ ነው ተባብለን አድረናል
ሁሉ ያንተ መሆኑን ዘንግተን ከኖርን
ብዙ አመት ሆኖናል፤
:
ይሄው ስማኝማ በባቢሎን
ምክንያት ሀጥያታችን በዝቶ፤
:
ቋንቋ ልሳናችን ለይተህ ቃኝተካል
ግድ የለም አሁን ግን ቋንቋችንን ቀማን
እንዳደርስብህ ግንቡ ይሻልካል፤
:
ይሄው ስማኝማ አንተን ልናከብር
የፈጠርክልን አንደበት ተዘጋ፤
:
አንተን ዘንግተናል ውዳሲያችን ሁሉ
ዘሬ ዘሬ ሆኖል በነጋ በጠባ
:
ግን ግን ይህ ህመም ምንድን ነው?
እንደምን ልወቀው?
ህመሜን እንዳልውጥ
ስቃዩ በዛብኝ እንዴት ልደብቀው
:
:
ግድ የለም ንገሩኝ
ህመሜ ምንድነው?
:
ጠሃይዋን እያየው ብርድ ብርድ የሚለኝ
በረዶ እየጣለ ሙቀት የሚገለኝ
ከቶ ምን ሆኜ ነው?
:
ወባ ነው እንዳልል
አጎበር ዘርግቼ፤
ብርድ ነው እንዳልል
ልብስ ደራርቤ
እሳትም አንድጄ ቤቴንም ዘግቼ፤
:
ለምን ይበርደኛል?
:
ለምን ይሞቀኛል?
:
እጅ እግሬ ጉልበቴስ
ምን ሆንኩኝ ብሎ ነው
'ሚቆረጣጥመኝ?
ምን ሆንኩኝ ብዬ ነው
ስኳር የሚመረኝ እሬት የሚጥመኝ?
:
ምን እንደሆንኩ እንጃ
:
የያዘኝ በሽታ ፈጣሪን ደፍሬ
እንዲህ ያስብለኛል፤
:
በልሙጥ ሰማይ ላይ ሰንደቄን ስላየው
ኮከቡን አጥፋልኝ ብዬ እጠይቃለው
ስሙን ባላውቀውም እውነት ታምሚያለው፤
:
ካስርቱ ትዛዛት አንድ የጨመርክበት
አልያም ያጎደልከው ሆኖ እየተሰማኝ
ህግ ሻርክ ብዬ መበታተን ጠማኝ፤
እንዲህም አስባለው
ስሙን ባላውቀውም እውነት ታምሜአለሁ
፡
ምን እንደሆንኩ እንጃ!
:
ህመሜን መለየት
ማወቁን አላውቀው፤
እንዳው ዝም ብዬ ነው
ቁስሌን እያየሁ
ትናንት ዛሬም ነገም
ሁሌም ምጠይቀው፤
:
ኬት መጣ ይህ ቁስል?
የት ነው የተጋጋጥሁ?
ወዴት ልዘል ይሆን
እግሬን ተሰብሬ
የስቃይ ምጥ ያማጥሁ
:
ምን እንደሆንኩ እንጃ!
:
እየጠዘጠዘኝ
እየቀዘቀዘኝ
እየገዘገዘኝ
:
የኔ ሰው እርቆኝ
ነው ጠላት የገነዘኝ፤
እያልኩ አስባለው
:
ከወዳጄም ጥል ነኝ
ከጠሌቴም ጥል ነኝ
ከራሴም ጋር ጥል ነኝ
:
እውነት ታምሜአለሁ
:
እንዲያው ዝም ብዬ እንጂ
:
እንደታመምኩኝስ
እንዳልታመምኩኝስ
ከወዴት አውቄው፤
እንዳው ላመል እንጂ
ጠይቅ ስለተባልኩ
እንዲህ ምጠይቀው፤
:
እንደዚህ እያልኩኝ!
:
ህመሜን ሰው ሁሉ
ስም እያወጣለት፤
ለየትኛው ህመም ክኒን ልዋጥለት፤
ለየትኛው ህመም መርፌ ልወጋለት።
እንጃ!
#አጭር_ልብወለድ
#የልጅነት_ዕይታ
ይህ ታሪክ የተከሰተው የሁለተኛ ክፍል ተማሪና የዘጠኝ ዓመት ልጅ እያለው ነው በወቅቱ ዱርዬው አባቴ እና ጭምቶ እናቴ በእኔ ላይ የፈጸሙትን አሻጥር ነው የምተርክላችሁ እለቱ ቅዳሜ 10 ሰዓት አካባቢ ነው አባቴ ና ዘመድ ጠይቀን እንምጣ ብሎኝ እናቴን በማስፈቀድ ይዞኝ ወጣ የምንሄደው ወንድሙ ጋር ነው እኛ ከምንኖርበት በመኪና የአንድ ሰዓት መንገድ ነው ፤ አድረን ነገ በማግስቱ እንድንመጣ ማለት ነው፡፡በጥም ነበር የፈነጠዝኩት አንደኛ ሁሌ ከአበቴ ጋር ሆኜ ወደ ሆነ ቦታ ስጓዝ በራስ መተማመኔ ይጨምራል.ሁለተኛ አጐቴ የእኔ እኩያ የሆነ ልጅ አለው ከእሱ ጋር በመጫወት የማሳልፈው ጊዜ ለእኔ ጣፋጭ ነው፡፡
ሄድን…አጐቴ ቤት ደረስን የአጐቴ ሚስት በጣም በጥሩ መስተንግዶ ነበር የተቀበለችን መክሰስ ቀረበልን.ቡና ተፈላ…12 ሰዓት አካባቢ ሲሆን አባቴ መጣው ተጫወት ብሎኝ ከቤት ሲወጣ እምቢ ብዬ ተከተልኩት.ግንባሩን ቢቆጥርብኝም…ሊያስፈራራኝ ቢሞክርም ምን እንደነካኝ አላውቅም ያለወትሮዬ እምቢኝ አልኩት..እንደ ፍላጐቱም ልታዘዝለት አልቻልኩም..በመጨረሻም ብቻ ሳይመስለው..ሁለተኛ ይዞኝ እንደማይመጣ እየዛተብኝ ይዞኝ ሄደ፡፡‹‹ የት ይዞህ ሄደ አትሉኝ…?››ሆነች ቀይ ወፈር ያለች…አዲስ የሚያምር ቀሚስ የለበሰች ሴትዬ ቤት እሱን ስታየው በደስታ ተፍነከነከች ጉንጭ ለጉንጭ ተሳሳሙና ወደ እኔ ጐንበስ ብላ አገላብጣ ሳመችኝ..ልትስመኝ ጐንበስ ባለችበት ወቅት ከሁለት የተቀሰሩ ቀይ ጡቶቾ ስንጥቅ መሀከል የሚመነጭ የሚመስል ደስ ሚል ሽታ ተበትኖ በአፍና በአፍንጫዬ ተመሰገብኝ…
‹‹የቀረህ መስሎኝ እኮ ተበሳጭቼብህ ነበር››አለችው ‹‹እመጣለው ብዬሽ ጨክኜ እንዴት እቀራለው?››አላት..ወደእኔ ገልመጥ እለ
‹‹ልጅህ ደግሞ አንተን ይመስላል ››አለችው እኔን እኔን እያች
‹‹ታዲያ እኔ ወልጄው ማንን እንዲመስልልሽ ትፈልጊያለሽ?››አላት..
ለምን እንደሆነ አላውቅም ሁሌ አባትህን ነው የምትመስለው ሲሉኝ እግዚያብሄርነው ነው ምትመስለው እንዳሉኝ ነገር ትንሾ ልቤ በድስታ ትንፈራፈራለች ሴትዬዋ እኛን አስቀምጣ ወደ ጐዲያ ገባችና ሲኒዋን ይዛ በመምጣት አቀራረበች ….ከሰል አቀጣጠለች..እጃችንን አስታጠበችን ና ሚያስጐመዥ የዶሮ ወጥ አቀረበችልን፡፡
‹‹ብሉ… ብሉ…..››ስትል
‹‹ነይ አንቺም ቁጭ በይ አላት››አባቴ ቀብረር ብሎ
‹‹ቡናውን ብቆላ አይሻልም ብለህ ነው?›› አለችው.. ግን ሁኔታዋን ሲያዬት ከእኛ ጋር ቁጭ ብላ ለመብላት የቋመጠች ትመስላለች
‹‹ተይ ባክሽ ይደርሳል››ሲላት ብዙም ሳታቅማማ ኩርሲዋን ይዛ በመምጣት በእሱ እና በእኔ መሀከል ተሰክታ ቁጭ አለች በፈገግታዋ እና ባቀረበችልን ሚያስጐመዥ ዶሮ ወጥ ያስደሰተችኝ ቢሆንም በመሀከላችን በመሰካቶ ግን ቅር አሰኝታኛለች..እንኳን ሌላ ሴት ይቅርና እናቴ እንኳን ከአባቴ ስታርቀኝ ደስ አይለኝም ነበር..እውነቱን ንገረን ካላችሁኝ ግን ብዙውን ጊዜ ቅር ይለኝ የነበረው በእኔና በእናቴ መሀከል አባቴ ሲሰነቀር ነው .አባቴ ከእናቴ ሲያርቀኝ ያበሽቀኛል…ልክ አሁን ይህቺ ሴትዬ እንዳበሸቀችኝ፡፡
አባቴ ምግቡን ደህና አድርጐ ጠቀለለና ይጐርሳል ብዬ ስጠብቅ ለእሷ አጐረሳት…. እሷም የመጀመሪያውን ጉርሻ አጐረሰችው ፈጥጬ የሁለቱን ጉርሻ ቅብብል በማየት ስቁለጨለጭ ‹‹ብላ እንጂ ምን ያደፈዝሀል?›› በሚል የቁጣ ይሁን የትዕዛዝ ባለየለት ንግግር አስበረገገኝ ታምረኛው አባቴ ፡፡
‹‹ወይ አፈር ስሆን እረሳንህ አይደል›› በብጣቂ እንጀራ ወጥ ነካ ነካ አድርጋ እኔንም አጐረሰችኝ ፡፡የአባቴ ሁኔታ ግን በጣም ገርሞኛል እናቴን ብቻ ይመስለኝ ነበር እንደዛ የሚያጐርሰው..ለካ ሌሎችንም ሴቶች በተመሳሳይ ሁኔታ ያጐርሳል…ድግሞ እኮ ‹‹…እኔ ከአንቺ ውጭ እኮ ማጉረስም መጉረስም አልወድም›› እያለ ለእናቴ ጉራውን ሲነፋ ስንት ቀን ሰምቼዋለው መሰላችሁ…ይሄኔ ይቺንም እንደዛ ብሎት ይሆናል? ዳሩ ምን አገባኝ አርፌ ጣፋጩን ምግብ አልበላም…ምግቡን በልተን ካጋመስን ቡኃላ አንድ አንድ እንቁላል ፊታችን አስቀመጠች…እሱን እየፈረካከስን ስንበላ ለአባቴ ደገመችለት ለእኔም ድጋሜው ይደርሰኛል ብዬ ስቁለጨለጭ ዘለለችኝና በምትኩ ስጋ ያዘለ አጥንት ፊት ለፊታችን ደረደረች፤ እሱን መጋጥ ጀመርኩ ቀጥሎ አባቴ ‹‹በቃኝ…. በቃኝ ››ሲላት
‹‹ቆይ እንጂ መቋደሻውስ ?››አለችና የሆነ ስጋ በማውጣት በእጆ አንጠልጥላ ወደ እሱ ዘረጋችለት እሱም አንደኛውን ጫፍ ያዘ ሁለቱም ወደ ራሳቸው ሳብትና ጠመዘዙት ሁለት ቦታ ተከፈላ እሷ እጅ ላይ የቀረውን ለእሱ ስታጐርሰው የእሱን ደግሞ ለእሷ አጐረሳት…‹‹ ምን ያሽቃብጡብኛል?… የየራሳቸውን ለየራሳቸው አይጐርሱም እንዴ..?››ስል አሰብኩ በልቤ ግን ምን ያሽቃብጡብኛል ማለት ምን ማለት ነው? እኔ እናጃ ብቻ የሆነ ሰው የሆነ ቦታ ይህቺን ቃል ለእንደዚህ አይነት ድርጊት ሲጠቀምባት ሰምቼ ይሆናል..የሆነ ሆኖ ጠገብንና ምግቡ ተነሳ ብና ተፈላ ጠጣን….ኸረ ተሳስቼ ነው እነሱ ናቸው የጠጡት እኔ አልጠጣውም..ዳግሞ አንድ የዘለልኩት ነገር አለ የሆ የፈረንጅ አረቄ ነው ብላ በትንሾ ብርጭቆ ሞልታ ሰጠችው..
‹‹ ጅን ትወዳለህ አይደል?›› እያለች
‹‹አዎ ግን..!››
‹‹ግን ምን ?ባክህ አትፍራው አያሰክርህም… ለዛ ነገርም አሪፍ ነው ሲሉ ሰምቼያለው››አለችው.ለየትኛው ነገር እንደሆነ ግን ለእኔ ሊገባኝ ባይችልም
‹‹አኸ!! ለራስሽ ብለሽ ነዋ ያዘጋጀሽው?››
‹‹አነተ..አረ አበልጆቼ አክፋይ ሲመጡ አምጥተውልኝ ነው…ሆሆሆ..!!!እንዲሁ በባዶውስ መች ቻልኩህ?›››አለችውና ለምን እንደሆነ አላውቅም ደንግጣ ወደእኔ አየች እሱንም ሳየው ምቾት አይነበብበትም
‹‹.ደግሞ መች ቻልኩህ ስትል ምን ለማለት ፈልጋ ነው ?ነው ወይስ ይዋጣልን ተባብለው ይደባደቡ ይሆን?››ብዙ ጊዜ የትልልቅ ሰዎች ወሬ ለምን እንደሚወሳሰብ አይገባኝም….ከምሽቱ አንድ ሰዓት አካባቢ ሲሆን አፍ ለአፍ ገጥመው ትንሽ በመንሾካሾክ ልሰማው ያልቻልኩትን ነገር ከተነጋገሩ በኃላ እኔና አባቴ ተያይዘን ወደ አጐቴ ቤት ተመለስን ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ቡኃላ አባቴ ድንገት ሹልክ ብሎ ጠፋ….ከአጐቴ ልጅ ጋር እየተጫወትኩ እና እየተላፋው ልጠብቀው ብሞክርም የውሀ ሽታ ሆኖ ቀረ… እኔም ድካም አዛለኝና በእንቅልፍ ተሸነፍኩና ተኛው..ጥዋት ስነሳም አልመጣም
ግራ ገባኝ ‹‹ጥሎኝ ወደ ቤት ተመለሰ እንዴ….?››የአጐቴን ሚስት ጠየቅኮት
‹‹አይ አለ እዚሁ ነው አረፋፍዶ ይመጣል››አለቺኝ ቅሬታ በሚነበብበት ፊት…
እኔ ግን ከዚህ በላይ በትዕግስት ልጠብቀው አልፈለግኩም….አረሳሳውና ማንም ሳያየኝ ሹልክ ብዬ ወደ ትናንትናዋ ሴትዩ ቤት አመራው
ስደርስ አባቴ እንደ ትናንትናው መቀመጫ ላይ ሳይሆን ሴትዬዋ አልጋ ላይ ጉብ ብሎል..ስሩ ያለው ጠረጰዛ ላይ በጓዱጓዳ ሰሀን ትኩስ እንፋሎቱ ከላዩ ላይ መትነን ያላቆመ ገንፎ ቀርቦለታል..እሷም ከጐኑ ቁጭ ብላ እየተጐራረሱ ሳለ ነበር ድንገት ዘው ያልኩባቸው ሁለቱም ብትን ብለው ነው የደነገጡት
‹‹እንዴ ምን ሆንክ ?››አለኝ
‹‹ጠፋህብኛ››መለስኩለት
‹‹ከልጆቹ ተጣላህ እንዴ?››
‹‹አልተጣላውም ግን ጠፋህብኝ››ደግሜ ያንኑ ዓረፍተ ነገር በመናገር ወቀሳዬን አጠናከርኩ
‹‹ና ግባ ቁጭ በል ከአባትህ ጐን››አለቺኝና ሌላ ማንኪያ አምጥታ አስጨበጠቺኝ በልተን ከጨረስን ቡኃላ እሷንም ሆነ የአጐቴን ቤተሰቦች ተሰናብተኝ የመልስ ጉዞ ወደ ቤት እንደደረስን አባቴ በቁሙ እኔን እቤት አስገባኝና ወጥቶ ወደ ዙረቱ ሄደ እናቴ ልጄ እርቦታል ብላ በቆንጆ ሁኔታ ከሰራቸው ልሙጥ ሽሮ በግማሽ እንጃራ ላይ ፈሰስ አድርጋ
አቀ
#የልጅነት_ዕይታ
ይህ ታሪክ የተከሰተው የሁለተኛ ክፍል ተማሪና የዘጠኝ ዓመት ልጅ እያለው ነው በወቅቱ ዱርዬው አባቴ እና ጭምቶ እናቴ በእኔ ላይ የፈጸሙትን አሻጥር ነው የምተርክላችሁ እለቱ ቅዳሜ 10 ሰዓት አካባቢ ነው አባቴ ና ዘመድ ጠይቀን እንምጣ ብሎኝ እናቴን በማስፈቀድ ይዞኝ ወጣ የምንሄደው ወንድሙ ጋር ነው እኛ ከምንኖርበት በመኪና የአንድ ሰዓት መንገድ ነው ፤ አድረን ነገ በማግስቱ እንድንመጣ ማለት ነው፡፡በጥም ነበር የፈነጠዝኩት አንደኛ ሁሌ ከአበቴ ጋር ሆኜ ወደ ሆነ ቦታ ስጓዝ በራስ መተማመኔ ይጨምራል.ሁለተኛ አጐቴ የእኔ እኩያ የሆነ ልጅ አለው ከእሱ ጋር በመጫወት የማሳልፈው ጊዜ ለእኔ ጣፋጭ ነው፡፡
ሄድን…አጐቴ ቤት ደረስን የአጐቴ ሚስት በጣም በጥሩ መስተንግዶ ነበር የተቀበለችን መክሰስ ቀረበልን.ቡና ተፈላ…12 ሰዓት አካባቢ ሲሆን አባቴ መጣው ተጫወት ብሎኝ ከቤት ሲወጣ እምቢ ብዬ ተከተልኩት.ግንባሩን ቢቆጥርብኝም…ሊያስፈራራኝ ቢሞክርም ምን እንደነካኝ አላውቅም ያለወትሮዬ እምቢኝ አልኩት..እንደ ፍላጐቱም ልታዘዝለት አልቻልኩም..በመጨረሻም ብቻ ሳይመስለው..ሁለተኛ ይዞኝ እንደማይመጣ እየዛተብኝ ይዞኝ ሄደ፡፡‹‹ የት ይዞህ ሄደ አትሉኝ…?››ሆነች ቀይ ወፈር ያለች…አዲስ የሚያምር ቀሚስ የለበሰች ሴትዬ ቤት እሱን ስታየው በደስታ ተፍነከነከች ጉንጭ ለጉንጭ ተሳሳሙና ወደ እኔ ጐንበስ ብላ አገላብጣ ሳመችኝ..ልትስመኝ ጐንበስ ባለችበት ወቅት ከሁለት የተቀሰሩ ቀይ ጡቶቾ ስንጥቅ መሀከል የሚመነጭ የሚመስል ደስ ሚል ሽታ ተበትኖ በአፍና በአፍንጫዬ ተመሰገብኝ…
‹‹የቀረህ መስሎኝ እኮ ተበሳጭቼብህ ነበር››አለችው ‹‹እመጣለው ብዬሽ ጨክኜ እንዴት እቀራለው?››አላት..ወደእኔ ገልመጥ እለ
‹‹ልጅህ ደግሞ አንተን ይመስላል ››አለችው እኔን እኔን እያች
‹‹ታዲያ እኔ ወልጄው ማንን እንዲመስልልሽ ትፈልጊያለሽ?››አላት..
ለምን እንደሆነ አላውቅም ሁሌ አባትህን ነው የምትመስለው ሲሉኝ እግዚያብሄርነው ነው ምትመስለው እንዳሉኝ ነገር ትንሾ ልቤ በድስታ ትንፈራፈራለች ሴትዬዋ እኛን አስቀምጣ ወደ ጐዲያ ገባችና ሲኒዋን ይዛ በመምጣት አቀራረበች ….ከሰል አቀጣጠለች..እጃችንን አስታጠበችን ና ሚያስጐመዥ የዶሮ ወጥ አቀረበችልን፡፡
‹‹ብሉ… ብሉ…..››ስትል
‹‹ነይ አንቺም ቁጭ በይ አላት››አባቴ ቀብረር ብሎ
‹‹ቡናውን ብቆላ አይሻልም ብለህ ነው?›› አለችው.. ግን ሁኔታዋን ሲያዬት ከእኛ ጋር ቁጭ ብላ ለመብላት የቋመጠች ትመስላለች
‹‹ተይ ባክሽ ይደርሳል››ሲላት ብዙም ሳታቅማማ ኩርሲዋን ይዛ በመምጣት በእሱ እና በእኔ መሀከል ተሰክታ ቁጭ አለች በፈገግታዋ እና ባቀረበችልን ሚያስጐመዥ ዶሮ ወጥ ያስደሰተችኝ ቢሆንም በመሀከላችን በመሰካቶ ግን ቅር አሰኝታኛለች..እንኳን ሌላ ሴት ይቅርና እናቴ እንኳን ከአባቴ ስታርቀኝ ደስ አይለኝም ነበር..እውነቱን ንገረን ካላችሁኝ ግን ብዙውን ጊዜ ቅር ይለኝ የነበረው በእኔና በእናቴ መሀከል አባቴ ሲሰነቀር ነው .አባቴ ከእናቴ ሲያርቀኝ ያበሽቀኛል…ልክ አሁን ይህቺ ሴትዬ እንዳበሸቀችኝ፡፡
አባቴ ምግቡን ደህና አድርጐ ጠቀለለና ይጐርሳል ብዬ ስጠብቅ ለእሷ አጐረሳት…. እሷም የመጀመሪያውን ጉርሻ አጐረሰችው ፈጥጬ የሁለቱን ጉርሻ ቅብብል በማየት ስቁለጨለጭ ‹‹ብላ እንጂ ምን ያደፈዝሀል?›› በሚል የቁጣ ይሁን የትዕዛዝ ባለየለት ንግግር አስበረገገኝ ታምረኛው አባቴ ፡፡
‹‹ወይ አፈር ስሆን እረሳንህ አይደል›› በብጣቂ እንጀራ ወጥ ነካ ነካ አድርጋ እኔንም አጐረሰችኝ ፡፡የአባቴ ሁኔታ ግን በጣም ገርሞኛል እናቴን ብቻ ይመስለኝ ነበር እንደዛ የሚያጐርሰው..ለካ ሌሎችንም ሴቶች በተመሳሳይ ሁኔታ ያጐርሳል…ድግሞ እኮ ‹‹…እኔ ከአንቺ ውጭ እኮ ማጉረስም መጉረስም አልወድም›› እያለ ለእናቴ ጉራውን ሲነፋ ስንት ቀን ሰምቼዋለው መሰላችሁ…ይሄኔ ይቺንም እንደዛ ብሎት ይሆናል? ዳሩ ምን አገባኝ አርፌ ጣፋጩን ምግብ አልበላም…ምግቡን በልተን ካጋመስን ቡኃላ አንድ አንድ እንቁላል ፊታችን አስቀመጠች…እሱን እየፈረካከስን ስንበላ ለአባቴ ደገመችለት ለእኔም ድጋሜው ይደርሰኛል ብዬ ስቁለጨለጭ ዘለለችኝና በምትኩ ስጋ ያዘለ አጥንት ፊት ለፊታችን ደረደረች፤ እሱን መጋጥ ጀመርኩ ቀጥሎ አባቴ ‹‹በቃኝ…. በቃኝ ››ሲላት
‹‹ቆይ እንጂ መቋደሻውስ ?››አለችና የሆነ ስጋ በማውጣት በእጆ አንጠልጥላ ወደ እሱ ዘረጋችለት እሱም አንደኛውን ጫፍ ያዘ ሁለቱም ወደ ራሳቸው ሳብትና ጠመዘዙት ሁለት ቦታ ተከፈላ እሷ እጅ ላይ የቀረውን ለእሱ ስታጐርሰው የእሱን ደግሞ ለእሷ አጐረሳት…‹‹ ምን ያሽቃብጡብኛል?… የየራሳቸውን ለየራሳቸው አይጐርሱም እንዴ..?››ስል አሰብኩ በልቤ ግን ምን ያሽቃብጡብኛል ማለት ምን ማለት ነው? እኔ እናጃ ብቻ የሆነ ሰው የሆነ ቦታ ይህቺን ቃል ለእንደዚህ አይነት ድርጊት ሲጠቀምባት ሰምቼ ይሆናል..የሆነ ሆኖ ጠገብንና ምግቡ ተነሳ ብና ተፈላ ጠጣን….ኸረ ተሳስቼ ነው እነሱ ናቸው የጠጡት እኔ አልጠጣውም..ዳግሞ አንድ የዘለልኩት ነገር አለ የሆ የፈረንጅ አረቄ ነው ብላ በትንሾ ብርጭቆ ሞልታ ሰጠችው..
‹‹ ጅን ትወዳለህ አይደል?›› እያለች
‹‹አዎ ግን..!››
‹‹ግን ምን ?ባክህ አትፍራው አያሰክርህም… ለዛ ነገርም አሪፍ ነው ሲሉ ሰምቼያለው››አለችው.ለየትኛው ነገር እንደሆነ ግን ለእኔ ሊገባኝ ባይችልም
‹‹አኸ!! ለራስሽ ብለሽ ነዋ ያዘጋጀሽው?››
‹‹አነተ..አረ አበልጆቼ አክፋይ ሲመጡ አምጥተውልኝ ነው…ሆሆሆ..!!!እንዲሁ በባዶውስ መች ቻልኩህ?›››አለችውና ለምን እንደሆነ አላውቅም ደንግጣ ወደእኔ አየች እሱንም ሳየው ምቾት አይነበብበትም
‹‹.ደግሞ መች ቻልኩህ ስትል ምን ለማለት ፈልጋ ነው ?ነው ወይስ ይዋጣልን ተባብለው ይደባደቡ ይሆን?››ብዙ ጊዜ የትልልቅ ሰዎች ወሬ ለምን እንደሚወሳሰብ አይገባኝም….ከምሽቱ አንድ ሰዓት አካባቢ ሲሆን አፍ ለአፍ ገጥመው ትንሽ በመንሾካሾክ ልሰማው ያልቻልኩትን ነገር ከተነጋገሩ በኃላ እኔና አባቴ ተያይዘን ወደ አጐቴ ቤት ተመለስን ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ቡኃላ አባቴ ድንገት ሹልክ ብሎ ጠፋ….ከአጐቴ ልጅ ጋር እየተጫወትኩ እና እየተላፋው ልጠብቀው ብሞክርም የውሀ ሽታ ሆኖ ቀረ… እኔም ድካም አዛለኝና በእንቅልፍ ተሸነፍኩና ተኛው..ጥዋት ስነሳም አልመጣም
ግራ ገባኝ ‹‹ጥሎኝ ወደ ቤት ተመለሰ እንዴ….?››የአጐቴን ሚስት ጠየቅኮት
‹‹አይ አለ እዚሁ ነው አረፋፍዶ ይመጣል››አለቺኝ ቅሬታ በሚነበብበት ፊት…
እኔ ግን ከዚህ በላይ በትዕግስት ልጠብቀው አልፈለግኩም….አረሳሳውና ማንም ሳያየኝ ሹልክ ብዬ ወደ ትናንትናዋ ሴትዩ ቤት አመራው
ስደርስ አባቴ እንደ ትናንትናው መቀመጫ ላይ ሳይሆን ሴትዬዋ አልጋ ላይ ጉብ ብሎል..ስሩ ያለው ጠረጰዛ ላይ በጓዱጓዳ ሰሀን ትኩስ እንፋሎቱ ከላዩ ላይ መትነን ያላቆመ ገንፎ ቀርቦለታል..እሷም ከጐኑ ቁጭ ብላ እየተጐራረሱ ሳለ ነበር ድንገት ዘው ያልኩባቸው ሁለቱም ብትን ብለው ነው የደነገጡት
‹‹እንዴ ምን ሆንክ ?››አለኝ
‹‹ጠፋህብኛ››መለስኩለት
‹‹ከልጆቹ ተጣላህ እንዴ?››
‹‹አልተጣላውም ግን ጠፋህብኝ››ደግሜ ያንኑ ዓረፍተ ነገር በመናገር ወቀሳዬን አጠናከርኩ
‹‹ና ግባ ቁጭ በል ከአባትህ ጐን››አለቺኝና ሌላ ማንኪያ አምጥታ አስጨበጠቺኝ በልተን ከጨረስን ቡኃላ እሷንም ሆነ የአጐቴን ቤተሰቦች ተሰናብተኝ የመልስ ጉዞ ወደ ቤት እንደደረስን አባቴ በቁሙ እኔን እቤት አስገባኝና ወጥቶ ወደ ዙረቱ ሄደ እናቴ ልጄ እርቦታል ብላ በቆንጆ ሁኔታ ከሰራቸው ልሙጥ ሽሮ በግማሽ እንጃራ ላይ ፈሰስ አድርጋ
አቀ
👍8
ረበችልኝ..ገና ሳየው ዘጋኝ
‹‹በቃኝ››
‹‹ምነው?››
‹‹አራበኝም..ገንፎ ብዙ ቅቤ ጭቅ ያለበት ጥግብ እስክል ነው የበላውት››አልኮት እንደ ቤተክርስቲያን ከበሮ የተወጠረውን ሆዴን ገልጬ እያስቃኘዋት
‹‹ይመኙሻል እኮ ጐበዝ ነች..እኔም የእሷ ገንፎ ናፍቆኛል››አለቺኝ ይመኙሻል ማት የአጐቴ ሚስት ነች‹‹የእሷን ገንፎ እኮ አይደለም የበላውት…. እነሱ ጋር ቁርስ ገንፎ ሳይሆን በሶ ነበር››
‹‹እና ታዲያ የት በላህ?››
‹‹ከአባዬ ጋር ሌላ ቦታ ሄደን ነው የበላነው›› የዚህን ጊዜ የእናቴ ጆሮ ለወሬ ሲቀሰር ታወቀኝ፡፡እኔ ደግሞ ለማወራው ወሬ ትኩረት ሲሰጡኝ ደስታዬ ይጨምራል የማውራት ሞራሌም ከገደብ ያልፋል
‹‹ሌላ ሴትዬ ማነች?››
‹‹ከእነ አጐቴ ቤት ወደታች በሚወስደው መንገድ ሀኪም ቤቱ ጋር ልትደርሺ ስትይ የሆነ ቀርከሀ አጥር ያለው ቤት የለም?››
‹‹አዎ አለ››
‹‹ከእሱ ቀጥሎ ደግሞ ኪወክስ ያለበት ቤት የለም?››
‹‹አዎ አለ››ጮክ ብላ በተሞጠጠ ትዕግስት
‹‹እዛ ቤት ፀዳለ የምትባል ሴት የለችም?››
‹‹አለች አልህ እኮ››አንቦረቀችብኝ….ግን እኮ አላላችኝም
እሷ ቤት ነው ገንፎ የበላነው እናቴ ተንጨረጨረች እናባዋ ሁሉ በዓይኖቾ ግጥም አለባት..እኔም በዛው ልክ ግራ ገባኝ… እስቲ የእኛ ገንፎ መብላት እሷን እንዴት ነው እንዲህ ሊበሳጫት የቻለው?ነው ወይስ ገንፎ ጥሩ አይደለም ሌላ ምግብ ለምን ሳታበላቸው ብላ ተናዳ ይሆን ?
‹‹ጥዋት ቁርስ ስለሆነ ነው እንጂ ማታ እኮ የሚጣፍጥ ዶሮ ወጥ… እንቁላል ስጋ ሁሉ ያለበት ነው የበላነው››
‹‹ይህቺ ናት እና ልጅት..ደግሳ ነዋ የጠበቀቻችሁ››
‹‹አዎ ደግ ሴት ነች ግን የሆነ ስጋ ላይ…››
‹‹እሺ የሆነ ስጋ ላይ ምን ሆነ?›.እናቴ ነች የወሬ ረሀቦ እያንቀጠቀጣት የጠየቀችኝ፡፡
‹‹ሁለቱ ብቻ እንደዚህ ከጫፍና ጫፍ ያዙና ጐትተው በመበጠስ ከተካፈሉ ብኃላ ለእኔ ሳይሰጡኝ ለራሷቸው ተጐራረሱ
‹‹መቋደሻም እስከመቋደስ ደርሰውልኛላ..የለውማ፡፡ እናትህን ነዋ ወስዶ ያስተዋወቀህ››
‹‹ኸረ እናቴ አይደለችም››ገና ለገና ለአንድ ቀን ዶሮ ወጥ እና ገንፎ ስላበላች እንዴት ነው አስናቴ የምትሆነው?››
‹‹ነች ባክህ››ብላኝ እቤቱን ጥላልኝ ወጣችና ወደ ጐሮ
የእናቴ የብስጭት መንስኤው ምንም ሊገባኝ አልቻለም…..ነው ወይስ ዶሮ ወጥ አምሮት ይሆን? ሴትዬዋን ለምኜት ይዤላት በመጣው ኖሮ… ብዬ ተቋጨው፡፡ ተነሳውና ወደ ጐሮ ተከተልኮት እያለቀሰች ነበር ፡፡ ሄድኩና ስሮ ቆምኩ ፈርቼያታለው..ትመታኛ ይሆን..?ብዬ ሳስብ ጭራሽ ወደ ራሷ ጐተተቺኝና ጉልበቶ ላይ አስተኝታኝ ፀጉሬን ታሻሽልኝ ጀመረ፡፡
‹‹ውሻዬ››
‹‹አቤት እማ››
‹‹ማታ ከማን ጋር ነው የተኛሀው …ፈራ ተባ እያለች በፍራቻ የጠየቀችኝ ጥያቄ እንደሆነ ያስታውቅባታል
‹‹ከነ ደጉ ጋር››መለስኩላት ደጉ ማለት እኩያዬ የሆነ የአጐቴ ልጅ ነው
‹‹አባትህስ?››
‹‹እሱ እኔ እንጃ የት እንዳደረ››
‹‹እንዴት?››
‹‹አላውቅማ… ማታ መጣው ብሎ ወጣና ቆየብኝ እኔ እንቅልፍ ወሰደኝ ፡፡ጥዋት ስነሳ እቤት የለም እና ፈለግኩትና ሳጣው እዛ ሴትዬዋ ጋር ሄድኩ.. አልጋዋ ላይ ቁጭ ብሎ ገንፎ ሲበላ ደረስኩ … ከዛ እኔም አብሬያቸው በላው››
ከዛ ኃላ እናቴ ፀጥ አለች፡፡ከተወሰነ ቆይታ ብኃላ ከተቀመጥንበት ተነሳንና ወደቤት ገባን..ትልቁን ሻንጣ አወጣችና የእሷን እና የእኔን ልብስ ብቻ እየመረጠች ትጠቀጥቅ ጀመር ….ግራ ገባኝ
‹‹እማ የት ልንሄድ ነው?››አልኮት
‹‹አያቶችህ ጋር››አለቺኝ ለስለስ ብላ..ደስ አለኝ በህይወቴ አያቶቼ ጋር እንደመሄድ የሚያስደስተኝ ነገር የለም
‹‹ግን ትምህርቴስ?››
‹‹አስፈቅድልሀለው›› ብላ አረጋጋችኝ
ሌላ የሚያሳስብ ሀሳብ ደግሞ በአዕምሮዬ መጣብኝ
‹‹አባዬስ ከእኛ ጋር ይሄዳል?››
‹‹ሁለታችን ብቻ ነን የምንሄደው››
‹‹ግን ምሳ ምናምን ማን ይሰራለታል?››
‹‹አይዞህ አታስብ አፀደ ጋር ሄዶ ይበላል››አለቺኝ
ሻንጣውን ጠቅጥቃ ዚፑን ዘጋግታ ከጨረሰች ቡኃላ ሻንጣውን ወደ በራፍ ጐትታ ለጉዞ እና ለነገር ዝግጁ ሆና አባቴን ትጠብቅ ጀመር፡፡
ቀጠዩ እና የመጨረሻው ምእራፍ ነገ ይቀጥላል
ብዙም ዛይቆይ አንድ የእናቴ ጓደኛ ወደ ቤታችን መጣች፡፡
‹‹ምን ሆነሽ ነው አይንሽ ያባበጠው?››እናቴን በማዳነቅ ጠየቀቻት
‹‹አይ ምንም አልሆንኩ…ዝም ብዬ ነው››
‹‹እንዴት ዝም ብለሽ ?አይንሽ እኮ ደም ለብሷል››
‹‹ቁጭ በይ ባክሽ›› አለቻት እናቴ ቆማ በጥያቄ ምታፋጥጣትን ጐደኛዋን…ልትቀመጥ ወደመቀመጫዋ ስትሄድ ዓይኖቾ ለጉዞ ዝግጁ የሆነው ሻንጣ ላይ አረፈ
‹‹እንዴ !!!ሻንጣ የት ለመሄድ?››
‹‹ወደቤተሰቦቼ ››
ኸሀ ገባኝ..ከባልሽ ጋር ተጣላቹ ማለት ነው?››
ዝም አለች እናቴ
‹‹ንገሪኝ እንጂ ምን ይዘጋሻል..ከእኔ ምን ምደብቂው ነገር አለሽ?››
‹‹ባክሽ ሰውዬው ፀዳለ ምትባል ሴት ወሽሞል አሉ››አለቻት…‹‹መወሸም ››ማለት ምን ማት ነው? አልገባኝም..ግን የሆነ መጥፎና የሚያናድድ ነገር እንደሆነ ገባኝ፡፡
‹‹ አትይኝም…ውይ ወንዶች!!!!›› ከእናቴ በላይ ተንዘረዘረች
‹‹ይሄውልሽ እንዲህ ተጫወተቨብኝ እልሻለው››
‹‹ለመሆኑ ካንቺ ምን አጣው ብሎ ነው?››አለቻት በከፍተኛ ማዳነቅ አፎን በእጆቾ አፍና
‹‹ያንቺስ ባል አንቺን ጥሎ ቤቱን እና ልጆቹን ጥሎ ሌላ አግብቶ የሄደው ካንቺ ምን አጥቶ ነው?››አናዳጅ ጥያቄዋን በአናዳጅ ጥያቄ መለሰችላት
‹‹እሱስ እውነትሽን ነው…ወንዶች ሲባሉ ያቺንም.. ያቺንም መልከፍ የሚወዱ ውሾች አይደሉ››
‹‹እና እንደዛው ነው››
‹‹እና ምን ልታደርጊ ነው?›.
‹‹በቃ ልጄን ይዤ ወደቤተሰቦቼ እሄዳለው….ከፈለገ ያምጣትና አብሮ ይኑር››
‹‹ጐበዝ..የታባቱ!!1 ይብላኝ ለእሱ እንጂ አንቺስ ደህና ቤተሰቦች አሉሽ..በዛ ላይ ገና ነሽ የፈለግሽውን ማግባት ትችያለሽ››አትል መሰላችሁ ስሬ ያለውን የውሀ ብርጭቆ አንስጬ ግንባሮን ብተረክክላት ደስ ይለኝ ነበር…እየሰማው አባቴን ‹ምናባቱ› ብላ ፊቴ ትሰድነበዋለች በጣም አናደደችኝ፡፡
‹‹አረ የምናባቱ ማግባት..ሁለታኛ…አርፌ ልጄን አሳድጋለው..ብቻ በሰላም ይልቀቀኝ እንጂ››
‹‹እሱማ ያው ሽማጊሌ ማንጋጋቱ አይቀርም››ቀጠለች ጐደኛ ተብዬዋ
‹‹…አይ እንዴት አንጀቴ እንዳረረ አታውቂም…. እንኮን የሰው ሽማግሌ ይቅርና እግዚያብሄርን ቢልክ አልሰማው፡፡ታውቂያለሽ አይል..ይሄ እኮ የመጀመሪያው አይደለም ከዚህ በፊትም ተመሳሳይ በደል በድሎኝ ለልጄ ስል ነበር በመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ይቅር ያልኩት አሁንማ እራስን ማስናቅና የእሱ መጫወቻ መሆን ነው..በሽታውን ተሸክሞብኝ መጥቶ ልጄን እንዳላሳደግ አጉል ቢያደርገኝስ?››
‹‹እና ጥዋት ልትሄጂ ነው?››
‹‹አዋ አሁንም መኪና አላገኝም እንጂ እዚህች ቤት ማደር አልፈልፈግም ነበር››
‹‹ይሁን እስቲ እኔም ሰሞኑን ስለምመጣ ጠይቅሻለው አይዞሽ በርቺ እንደእኔ ጥሎሽ ከመውጣቱ በፊት አንቺ ቀድመሽው ጥለሽው መውጣትሽ አሪፍ ነው››ብላ የውሳኔዋን ትክክለኝነት አረጋገጠችላት እና እናቴን አበረታታ እና ተሰናብታ ከቤት እንደወጣች እኔም ከኃላ ዋ ተከትዬት እቤቱን ለቅቄ ወጣው ነገ ወደ አያቶቼ መሄዴ ቁርጥ ጉዳይ ስለሆነ ጐደኞቼን ለመሰናበት…ስዞር ቆይቼ ሲጨልም ወደቤት ተመለስኩ አባቴ አልመጣም እናቴ ሰውነቴን አጥባ እራቴን አብልታኝ ‹‹ በለሊት ስለምንነሳ በጊዜ ተኛ›› ብላ አስተኛችኝ ረጅም ቀን አሰዋልፌ ስለነበር ወዲያው እንቅልፍ ወሰደኝ ስንት ሰዓት እንደሆነ አላውቅም በግምት ከለሊቱ 5 ወይም 6 ሰዓት ይሆን ይመስለኛል ሀይለኛ የበር መንጐጐት ከእንቅልፌ አባነነኝ
‹‹በቃኝ››
‹‹ምነው?››
‹‹አራበኝም..ገንፎ ብዙ ቅቤ ጭቅ ያለበት ጥግብ እስክል ነው የበላውት››አልኮት እንደ ቤተክርስቲያን ከበሮ የተወጠረውን ሆዴን ገልጬ እያስቃኘዋት
‹‹ይመኙሻል እኮ ጐበዝ ነች..እኔም የእሷ ገንፎ ናፍቆኛል››አለቺኝ ይመኙሻል ማት የአጐቴ ሚስት ነች‹‹የእሷን ገንፎ እኮ አይደለም የበላውት…. እነሱ ጋር ቁርስ ገንፎ ሳይሆን በሶ ነበር››
‹‹እና ታዲያ የት በላህ?››
‹‹ከአባዬ ጋር ሌላ ቦታ ሄደን ነው የበላነው›› የዚህን ጊዜ የእናቴ ጆሮ ለወሬ ሲቀሰር ታወቀኝ፡፡እኔ ደግሞ ለማወራው ወሬ ትኩረት ሲሰጡኝ ደስታዬ ይጨምራል የማውራት ሞራሌም ከገደብ ያልፋል
‹‹ሌላ ሴትዬ ማነች?››
‹‹ከእነ አጐቴ ቤት ወደታች በሚወስደው መንገድ ሀኪም ቤቱ ጋር ልትደርሺ ስትይ የሆነ ቀርከሀ አጥር ያለው ቤት የለም?››
‹‹አዎ አለ››
‹‹ከእሱ ቀጥሎ ደግሞ ኪወክስ ያለበት ቤት የለም?››
‹‹አዎ አለ››ጮክ ብላ በተሞጠጠ ትዕግስት
‹‹እዛ ቤት ፀዳለ የምትባል ሴት የለችም?››
‹‹አለች አልህ እኮ››አንቦረቀችብኝ….ግን እኮ አላላችኝም
እሷ ቤት ነው ገንፎ የበላነው እናቴ ተንጨረጨረች እናባዋ ሁሉ በዓይኖቾ ግጥም አለባት..እኔም በዛው ልክ ግራ ገባኝ… እስቲ የእኛ ገንፎ መብላት እሷን እንዴት ነው እንዲህ ሊበሳጫት የቻለው?ነው ወይስ ገንፎ ጥሩ አይደለም ሌላ ምግብ ለምን ሳታበላቸው ብላ ተናዳ ይሆን ?
‹‹ጥዋት ቁርስ ስለሆነ ነው እንጂ ማታ እኮ የሚጣፍጥ ዶሮ ወጥ… እንቁላል ስጋ ሁሉ ያለበት ነው የበላነው››
‹‹ይህቺ ናት እና ልጅት..ደግሳ ነዋ የጠበቀቻችሁ››
‹‹አዎ ደግ ሴት ነች ግን የሆነ ስጋ ላይ…››
‹‹እሺ የሆነ ስጋ ላይ ምን ሆነ?›.እናቴ ነች የወሬ ረሀቦ እያንቀጠቀጣት የጠየቀችኝ፡፡
‹‹ሁለቱ ብቻ እንደዚህ ከጫፍና ጫፍ ያዙና ጐትተው በመበጠስ ከተካፈሉ ብኃላ ለእኔ ሳይሰጡኝ ለራሷቸው ተጐራረሱ
‹‹መቋደሻም እስከመቋደስ ደርሰውልኛላ..የለውማ፡፡ እናትህን ነዋ ወስዶ ያስተዋወቀህ››
‹‹ኸረ እናቴ አይደለችም››ገና ለገና ለአንድ ቀን ዶሮ ወጥ እና ገንፎ ስላበላች እንዴት ነው አስናቴ የምትሆነው?››
‹‹ነች ባክህ››ብላኝ እቤቱን ጥላልኝ ወጣችና ወደ ጐሮ
የእናቴ የብስጭት መንስኤው ምንም ሊገባኝ አልቻለም…..ነው ወይስ ዶሮ ወጥ አምሮት ይሆን? ሴትዬዋን ለምኜት ይዤላት በመጣው ኖሮ… ብዬ ተቋጨው፡፡ ተነሳውና ወደ ጐሮ ተከተልኮት እያለቀሰች ነበር ፡፡ ሄድኩና ስሮ ቆምኩ ፈርቼያታለው..ትመታኛ ይሆን..?ብዬ ሳስብ ጭራሽ ወደ ራሷ ጐተተቺኝና ጉልበቶ ላይ አስተኝታኝ ፀጉሬን ታሻሽልኝ ጀመረ፡፡
‹‹ውሻዬ››
‹‹አቤት እማ››
‹‹ማታ ከማን ጋር ነው የተኛሀው …ፈራ ተባ እያለች በፍራቻ የጠየቀችኝ ጥያቄ እንደሆነ ያስታውቅባታል
‹‹ከነ ደጉ ጋር››መለስኩላት ደጉ ማለት እኩያዬ የሆነ የአጐቴ ልጅ ነው
‹‹አባትህስ?››
‹‹እሱ እኔ እንጃ የት እንዳደረ››
‹‹እንዴት?››
‹‹አላውቅማ… ማታ መጣው ብሎ ወጣና ቆየብኝ እኔ እንቅልፍ ወሰደኝ ፡፡ጥዋት ስነሳ እቤት የለም እና ፈለግኩትና ሳጣው እዛ ሴትዬዋ ጋር ሄድኩ.. አልጋዋ ላይ ቁጭ ብሎ ገንፎ ሲበላ ደረስኩ … ከዛ እኔም አብሬያቸው በላው››
ከዛ ኃላ እናቴ ፀጥ አለች፡፡ከተወሰነ ቆይታ ብኃላ ከተቀመጥንበት ተነሳንና ወደቤት ገባን..ትልቁን ሻንጣ አወጣችና የእሷን እና የእኔን ልብስ ብቻ እየመረጠች ትጠቀጥቅ ጀመር ….ግራ ገባኝ
‹‹እማ የት ልንሄድ ነው?››አልኮት
‹‹አያቶችህ ጋር››አለቺኝ ለስለስ ብላ..ደስ አለኝ በህይወቴ አያቶቼ ጋር እንደመሄድ የሚያስደስተኝ ነገር የለም
‹‹ግን ትምህርቴስ?››
‹‹አስፈቅድልሀለው›› ብላ አረጋጋችኝ
ሌላ የሚያሳስብ ሀሳብ ደግሞ በአዕምሮዬ መጣብኝ
‹‹አባዬስ ከእኛ ጋር ይሄዳል?››
‹‹ሁለታችን ብቻ ነን የምንሄደው››
‹‹ግን ምሳ ምናምን ማን ይሰራለታል?››
‹‹አይዞህ አታስብ አፀደ ጋር ሄዶ ይበላል››አለቺኝ
ሻንጣውን ጠቅጥቃ ዚፑን ዘጋግታ ከጨረሰች ቡኃላ ሻንጣውን ወደ በራፍ ጐትታ ለጉዞ እና ለነገር ዝግጁ ሆና አባቴን ትጠብቅ ጀመር፡፡
ቀጠዩ እና የመጨረሻው ምእራፍ ነገ ይቀጥላል
ብዙም ዛይቆይ አንድ የእናቴ ጓደኛ ወደ ቤታችን መጣች፡፡
‹‹ምን ሆነሽ ነው አይንሽ ያባበጠው?››እናቴን በማዳነቅ ጠየቀቻት
‹‹አይ ምንም አልሆንኩ…ዝም ብዬ ነው››
‹‹እንዴት ዝም ብለሽ ?አይንሽ እኮ ደም ለብሷል››
‹‹ቁጭ በይ ባክሽ›› አለቻት እናቴ ቆማ በጥያቄ ምታፋጥጣትን ጐደኛዋን…ልትቀመጥ ወደመቀመጫዋ ስትሄድ ዓይኖቾ ለጉዞ ዝግጁ የሆነው ሻንጣ ላይ አረፈ
‹‹እንዴ !!!ሻንጣ የት ለመሄድ?››
‹‹ወደቤተሰቦቼ ››
ኸሀ ገባኝ..ከባልሽ ጋር ተጣላቹ ማለት ነው?››
ዝም አለች እናቴ
‹‹ንገሪኝ እንጂ ምን ይዘጋሻል..ከእኔ ምን ምደብቂው ነገር አለሽ?››
‹‹ባክሽ ሰውዬው ፀዳለ ምትባል ሴት ወሽሞል አሉ››አለቻት…‹‹መወሸም ››ማለት ምን ማት ነው? አልገባኝም..ግን የሆነ መጥፎና የሚያናድድ ነገር እንደሆነ ገባኝ፡፡
‹‹ አትይኝም…ውይ ወንዶች!!!!›› ከእናቴ በላይ ተንዘረዘረች
‹‹ይሄውልሽ እንዲህ ተጫወተቨብኝ እልሻለው››
‹‹ለመሆኑ ካንቺ ምን አጣው ብሎ ነው?››አለቻት በከፍተኛ ማዳነቅ አፎን በእጆቾ አፍና
‹‹ያንቺስ ባል አንቺን ጥሎ ቤቱን እና ልጆቹን ጥሎ ሌላ አግብቶ የሄደው ካንቺ ምን አጥቶ ነው?››አናዳጅ ጥያቄዋን በአናዳጅ ጥያቄ መለሰችላት
‹‹እሱስ እውነትሽን ነው…ወንዶች ሲባሉ ያቺንም.. ያቺንም መልከፍ የሚወዱ ውሾች አይደሉ››
‹‹እና እንደዛው ነው››
‹‹እና ምን ልታደርጊ ነው?›.
‹‹በቃ ልጄን ይዤ ወደቤተሰቦቼ እሄዳለው….ከፈለገ ያምጣትና አብሮ ይኑር››
‹‹ጐበዝ..የታባቱ!!1 ይብላኝ ለእሱ እንጂ አንቺስ ደህና ቤተሰቦች አሉሽ..በዛ ላይ ገና ነሽ የፈለግሽውን ማግባት ትችያለሽ››አትል መሰላችሁ ስሬ ያለውን የውሀ ብርጭቆ አንስጬ ግንባሮን ብተረክክላት ደስ ይለኝ ነበር…እየሰማው አባቴን ‹ምናባቱ› ብላ ፊቴ ትሰድነበዋለች በጣም አናደደችኝ፡፡
‹‹አረ የምናባቱ ማግባት..ሁለታኛ…አርፌ ልጄን አሳድጋለው..ብቻ በሰላም ይልቀቀኝ እንጂ››
‹‹እሱማ ያው ሽማጊሌ ማንጋጋቱ አይቀርም››ቀጠለች ጐደኛ ተብዬዋ
‹‹…አይ እንዴት አንጀቴ እንዳረረ አታውቂም…. እንኮን የሰው ሽማግሌ ይቅርና እግዚያብሄርን ቢልክ አልሰማው፡፡ታውቂያለሽ አይል..ይሄ እኮ የመጀመሪያው አይደለም ከዚህ በፊትም ተመሳሳይ በደል በድሎኝ ለልጄ ስል ነበር በመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ይቅር ያልኩት አሁንማ እራስን ማስናቅና የእሱ መጫወቻ መሆን ነው..በሽታውን ተሸክሞብኝ መጥቶ ልጄን እንዳላሳደግ አጉል ቢያደርገኝስ?››
‹‹እና ጥዋት ልትሄጂ ነው?››
‹‹አዋ አሁንም መኪና አላገኝም እንጂ እዚህች ቤት ማደር አልፈልፈግም ነበር››
‹‹ይሁን እስቲ እኔም ሰሞኑን ስለምመጣ ጠይቅሻለው አይዞሽ በርቺ እንደእኔ ጥሎሽ ከመውጣቱ በፊት አንቺ ቀድመሽው ጥለሽው መውጣትሽ አሪፍ ነው››ብላ የውሳኔዋን ትክክለኝነት አረጋገጠችላት እና እናቴን አበረታታ እና ተሰናብታ ከቤት እንደወጣች እኔም ከኃላ ዋ ተከትዬት እቤቱን ለቅቄ ወጣው ነገ ወደ አያቶቼ መሄዴ ቁርጥ ጉዳይ ስለሆነ ጐደኞቼን ለመሰናበት…ስዞር ቆይቼ ሲጨልም ወደቤት ተመለስኩ አባቴ አልመጣም እናቴ ሰውነቴን አጥባ እራቴን አብልታኝ ‹‹ በለሊት ስለምንነሳ በጊዜ ተኛ›› ብላ አስተኛችኝ ረጅም ቀን አሰዋልፌ ስለነበር ወዲያው እንቅልፍ ወሰደኝ ስንት ሰዓት እንደሆነ አላውቅም በግምት ከለሊቱ 5 ወይም 6 ሰዓት ይሆን ይመስለኛል ሀይለኛ የበር መንጐጐት ከእንቅልፌ አባነነኝ
👍7❤1
...እናቴ ሳያት ከመተኛቴ በፊት የተቀመጠችበት ቦታ እንደተቀመጠች ነው..እስከአሁን እንዳልተኛች በሁኔታዋ ያስታውቃል፡፡
‹‹አንቺ ሴትዬ አትሰሚም እንዴ?››የአባቴ ድምፅ ነው..ትንሽ ኮልተፍተፍ ብሎል፡፡ልከፍትለት ከአልጋዬ ስወርድ
‹‹አርፈህ ተኛ››ብላ አንቦረቀችብኝ..ከራማዬ ተገፈፈና ወደ መኝታዬ ተመለስኩ
‹‹ኸሀ… እየሰማሽ ነው ለካ..?ነው ወይስ ማልመጣ መስሎሽ ያስገባሽው ሰው አለ ?››
‹‹ሰው ሁሉ እንደአንተ ሸርሙጣ ይመስልሀል አይደለ?››ብለው እርፍ..ይ እንግዲህ ሰውን ቀና ብላ ማናገር እንኮን ከምትፈራው ከጭምቶ እናቴ የወጣ ዓረፍተ ነገር ነው
‹‹ሸርሙጣ…እኔ ሸርሙጥ?››ይሄንን በር ሳልገነጥለው ክፈቺ››አባቴ ድንፋታ መጠኑን ጨመረ
‹‹አልከፍትም..ትናንት ያሳደረችህን ጋር ሄደህ እደር››
በራፉን የተደረመሰ እስኪመስል ተነቃነቀ..እናቴ ተሸነፈችና በአቋሞ መፅናት አቅቶት የበራፉን መሸንጐሪያ ጐትታ አላቀቀችው..በር ወለል ብሎ ተበረገደ፡፡ አባቴም ተንደርድሮ ወደ ውስጥ እንደገባ መሀል ወለል ላይ የተገተረችውን እናቴን በጥፊ አላሳት..በርግጫ ደገማት..፡፡ በቅፅበት ቤቱ ቀውጢ ሆነ፤ እኔም እሪታዬን አስነካውት…የእሷን ጩኸት ማስቆም ሲያቅተው ወይም የእኔ ጩኸት ከእሷ ጩኸት በላይ ስለረበሸው ይመስለኛል ተንደርድሮ መጣና በዛ ሰፊድ እጁ አንዴ በጥፊ ሲያልሰኝ ፀጥ አልኩ ..በቃ ድዳ ሆንኩ፡፡እናቴ ግን ጭራሽ አበደች‹‹ልጄን አትንካው..እኔኑ እንደጀመርክ ጨርሰኝ….ይሄውልህ…››በዚህን ጊዜ ጐረቤቶቻችን ከየአቅጣጫው የጩኸት ድምፅ ሰምተው ይመስለኛል እየተሮሮጡ ሲመጡ ተሰማ…..ደርሰው ቤታችንን ደጃፍ አልፈው ወደ ውስጥ ገመዝለቃቸው በፊት አባቴ እየተንገዳገደ ሄዶ በራፉን ጠረቀመባቸው
እናቴ ‹‹አሳወጣኝ እዚህ ቤት አላድርም፣››ብትል ከውጭ ያሉት ሰዎች ‹‹በራፉን አንዴ ክፈትልን ››ብለው ቢማጸኑት..በራፉን ቢደበድቡ አንባገነኑ አባቴ ሊሰማቸው አልፈልግም፡፡ ቡኃላ እናቴ ተስፋ ስትቆርጥ መሰለኝ ጐረቤቶቾን‹‹ በቃ ወደ ቤታችሁ ግቡ… ብቻ ያደረገኝን ሁሉ በልቦናችሁ ይዙት ..ሞቼ ከተገኘውም እሱ እንደሆነ እወቁና ለዘመዶቼ ንገሩልኝ ሰላም ካደርኩ ነገ በህግ አንቀባርረዋለው..መንግስት ባለበት ሀገር እንዲህ አይጫወትብኝም..የሴቶች መፍት በተከበረበት ዘመን ላይ ነው ያለነው…››በማለት ከሰፊ መግለጫ ጋር እንዲሄዱ አደረገች፡፡ከዛ ቡኃላ ሲጨቃጨቁ ሲነታረኩ‹ ተኚ …አልተኛም፤ ልንካሽ …አትነካኝ› ሲባባሉ እኔ ሳዳምጥ ሳዳምጥ እነሱ ከመድከማቸው በፊት እኔ ዛልኩና እንቅልፍ ይዞኝ ጥግ አለ፡፡
…. ስባንን የጥዋት ፀሀይ በበራፋችን ስንጥቅ ወደ ቤት ገብቶ ሳሎናችንን አድምቆታል፡፡ አባቴ በጥፊ ያላሰኝ ፊቴ እየለበለበኝ ነው‹‹..እንዲህ አቃጥሎኝማ ሁለተኛ አላናግረውም ..አሁኑኑ ነው ጠዬው ወደ አያቴቶቼ ጋር እናቴን ተከትዬ የምሄደው…››በማለት ዓይኔን በመከራ ከፈትኩና ከአልጋዬ ወረድኩ..እናቴ ያሰናዳችው ሻንጣ እዛው በራፍ አካባቢ ዝግጁ እንደሆነ ነው
‹‹…እናቴ የት ሄደች..? እንዴት እስከአሁን አረፈደች…? በለሊት አልነበረ እንዴ እንሄዳለን ያለቺኝ?›› ግራ እንደተጋባው ዝም ብዬ ወደ ወላጆቼ መኝታ ቤት አመራው በራፉ አልተቀረቀረም ገርበብ እንዳለ ነው፡፡ገፋ አደረግኩና ወደ ውስጥ ገባው ጠላታችሁ ክው ይበል ክው ነው ያልኩት..ከዛን ቀን በፊት ሆነ ከዛ ቡኃላ በእንደዛ ዓይነት ሁኔታ ደንግጬ አላውቅም….ከወገብ በላይ ሁለቱም እርቃናቸውን ናቸው.. እቅፍቅፍ ብለው ከመጣበቃቸው የተነሳ ሁለት ጫንቅላት ያለው አንድ ሰው ነው የሚመስሉት፡፡የ ሁለቱም ልብስ ወለል ላይ ተዝረክርኮል፡፡በሁለቱም በጣም ተበሳጨው… በተለይ በእናቴ ፡፡አስጠሉኝ ፡፡ተመልሼ ወደ ሳሎን ገባው የእናቴን የገንዘብ ቦርሳ ጠረጵዛ ላይ አየውት… ከፈትኩት እና ከውስጡ የተወሰነ ብር ዛቅ አድርጌ ኪሴ ከተትኩ፡፡እናቴ ስትፎክርበት እና ስታስፈራራበት ያመሸችውን ትልቅ ሻንጣ ከፈትኩና ከውስጡ ራሴን ልብሶች መርጬ በትንሽ ፔስታል ጨመርኩና የሳሎኑን በር ከፍቼ ቤታቸውን ለቅቄላቸው ወጠው ፡፡ወደ መነኸሪያ..ሁለቱም ናቸው ያስጠሉኝ፡፡ እነደዛ ለእሷ ስል በጥፊ ተቃጥዬ ጭራሽ አቅፋው ትተኛለች..?ኸረ ከእነዚህ ጋር ማን ይኖራል…? አያቶቼ ይሻሉኛል፡፡
💫አለቀ💫
Like 👍እየቀነሰ ነው አትቆጥቡ😜
👍 እያረጋቹ
አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን
‹‹አንቺ ሴትዬ አትሰሚም እንዴ?››የአባቴ ድምፅ ነው..ትንሽ ኮልተፍተፍ ብሎል፡፡ልከፍትለት ከአልጋዬ ስወርድ
‹‹አርፈህ ተኛ››ብላ አንቦረቀችብኝ..ከራማዬ ተገፈፈና ወደ መኝታዬ ተመለስኩ
‹‹ኸሀ… እየሰማሽ ነው ለካ..?ነው ወይስ ማልመጣ መስሎሽ ያስገባሽው ሰው አለ ?››
‹‹ሰው ሁሉ እንደአንተ ሸርሙጣ ይመስልሀል አይደለ?››ብለው እርፍ..ይ እንግዲህ ሰውን ቀና ብላ ማናገር እንኮን ከምትፈራው ከጭምቶ እናቴ የወጣ ዓረፍተ ነገር ነው
‹‹ሸርሙጣ…እኔ ሸርሙጥ?››ይሄንን በር ሳልገነጥለው ክፈቺ››አባቴ ድንፋታ መጠኑን ጨመረ
‹‹አልከፍትም..ትናንት ያሳደረችህን ጋር ሄደህ እደር››
በራፉን የተደረመሰ እስኪመስል ተነቃነቀ..እናቴ ተሸነፈችና በአቋሞ መፅናት አቅቶት የበራፉን መሸንጐሪያ ጐትታ አላቀቀችው..በር ወለል ብሎ ተበረገደ፡፡ አባቴም ተንደርድሮ ወደ ውስጥ እንደገባ መሀል ወለል ላይ የተገተረችውን እናቴን በጥፊ አላሳት..በርግጫ ደገማት..፡፡ በቅፅበት ቤቱ ቀውጢ ሆነ፤ እኔም እሪታዬን አስነካውት…የእሷን ጩኸት ማስቆም ሲያቅተው ወይም የእኔ ጩኸት ከእሷ ጩኸት በላይ ስለረበሸው ይመስለኛል ተንደርድሮ መጣና በዛ ሰፊድ እጁ አንዴ በጥፊ ሲያልሰኝ ፀጥ አልኩ ..በቃ ድዳ ሆንኩ፡፡እናቴ ግን ጭራሽ አበደች‹‹ልጄን አትንካው..እኔኑ እንደጀመርክ ጨርሰኝ….ይሄውልህ…››በዚህን ጊዜ ጐረቤቶቻችን ከየአቅጣጫው የጩኸት ድምፅ ሰምተው ይመስለኛል እየተሮሮጡ ሲመጡ ተሰማ…..ደርሰው ቤታችንን ደጃፍ አልፈው ወደ ውስጥ ገመዝለቃቸው በፊት አባቴ እየተንገዳገደ ሄዶ በራፉን ጠረቀመባቸው
እናቴ ‹‹አሳወጣኝ እዚህ ቤት አላድርም፣››ብትል ከውጭ ያሉት ሰዎች ‹‹በራፉን አንዴ ክፈትልን ››ብለው ቢማጸኑት..በራፉን ቢደበድቡ አንባገነኑ አባቴ ሊሰማቸው አልፈልግም፡፡ ቡኃላ እናቴ ተስፋ ስትቆርጥ መሰለኝ ጐረቤቶቾን‹‹ በቃ ወደ ቤታችሁ ግቡ… ብቻ ያደረገኝን ሁሉ በልቦናችሁ ይዙት ..ሞቼ ከተገኘውም እሱ እንደሆነ እወቁና ለዘመዶቼ ንገሩልኝ ሰላም ካደርኩ ነገ በህግ አንቀባርረዋለው..መንግስት ባለበት ሀገር እንዲህ አይጫወትብኝም..የሴቶች መፍት በተከበረበት ዘመን ላይ ነው ያለነው…››በማለት ከሰፊ መግለጫ ጋር እንዲሄዱ አደረገች፡፡ከዛ ቡኃላ ሲጨቃጨቁ ሲነታረኩ‹ ተኚ …አልተኛም፤ ልንካሽ …አትነካኝ› ሲባባሉ እኔ ሳዳምጥ ሳዳምጥ እነሱ ከመድከማቸው በፊት እኔ ዛልኩና እንቅልፍ ይዞኝ ጥግ አለ፡፡
…. ስባንን የጥዋት ፀሀይ በበራፋችን ስንጥቅ ወደ ቤት ገብቶ ሳሎናችንን አድምቆታል፡፡ አባቴ በጥፊ ያላሰኝ ፊቴ እየለበለበኝ ነው‹‹..እንዲህ አቃጥሎኝማ ሁለተኛ አላናግረውም ..አሁኑኑ ነው ጠዬው ወደ አያቴቶቼ ጋር እናቴን ተከትዬ የምሄደው…››በማለት ዓይኔን በመከራ ከፈትኩና ከአልጋዬ ወረድኩ..እናቴ ያሰናዳችው ሻንጣ እዛው በራፍ አካባቢ ዝግጁ እንደሆነ ነው
‹‹…እናቴ የት ሄደች..? እንዴት እስከአሁን አረፈደች…? በለሊት አልነበረ እንዴ እንሄዳለን ያለቺኝ?›› ግራ እንደተጋባው ዝም ብዬ ወደ ወላጆቼ መኝታ ቤት አመራው በራፉ አልተቀረቀረም ገርበብ እንዳለ ነው፡፡ገፋ አደረግኩና ወደ ውስጥ ገባው ጠላታችሁ ክው ይበል ክው ነው ያልኩት..ከዛን ቀን በፊት ሆነ ከዛ ቡኃላ በእንደዛ ዓይነት ሁኔታ ደንግጬ አላውቅም….ከወገብ በላይ ሁለቱም እርቃናቸውን ናቸው.. እቅፍቅፍ ብለው ከመጣበቃቸው የተነሳ ሁለት ጫንቅላት ያለው አንድ ሰው ነው የሚመስሉት፡፡የ ሁለቱም ልብስ ወለል ላይ ተዝረክርኮል፡፡በሁለቱም በጣም ተበሳጨው… በተለይ በእናቴ ፡፡አስጠሉኝ ፡፡ተመልሼ ወደ ሳሎን ገባው የእናቴን የገንዘብ ቦርሳ ጠረጵዛ ላይ አየውት… ከፈትኩት እና ከውስጡ የተወሰነ ብር ዛቅ አድርጌ ኪሴ ከተትኩ፡፡እናቴ ስትፎክርበት እና ስታስፈራራበት ያመሸችውን ትልቅ ሻንጣ ከፈትኩና ከውስጡ ራሴን ልብሶች መርጬ በትንሽ ፔስታል ጨመርኩና የሳሎኑን በር ከፍቼ ቤታቸውን ለቅቄላቸው ወጠው ፡፡ወደ መነኸሪያ..ሁለቱም ናቸው ያስጠሉኝ፡፡ እነደዛ ለእሷ ስል በጥፊ ተቃጥዬ ጭራሽ አቅፋው ትተኛለች..?ኸረ ከእነዚህ ጋር ማን ይኖራል…? አያቶቼ ይሻሉኛል፡፡
💫አለቀ💫
Like 👍እየቀነሰ ነው አትቆጥቡ😜
👍 እያረጋቹ
አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን
👍8😁4
#የመልስ_ጉዞ_ወደመነሻ
:
#ክፍል_ሁለት
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
...ኢትዬጵያን በዩቶፐያ ፅንሰ ሀሳብ ዳግም መገንባት ከአያቴ የወረስኩት ህልሜ እና ዓላማዬ እንደሆነ ነግሬያችኃለው …ግን እንዴት አድርጌ ነው የማሳካው …?እንደማሳክው የማምነው ከራሴ በላይ በሚስቴ እምነት ስላለኝ ነው፡፡ሚስቴ …የዋናው የታሪኬ ማጠንጠኛ እሷ ነች፡፡እሷ ደግሞ መንፈስ ነች፡፡ገራሚ መንፈስ፡፡አስፈሪ መንፈስ፤ታሪካዊ መንፈስ፤አፍዛዥ መንፈስ…ሁሉን አድራጊ ፈላጭ ቆራጭ መንፈስ፡፡አዎ ስለእሷ የምነግራችሁ ነገር ቢኖር የደረስኩበትን እና ያወቅኩትን ብቻ ነው፡፡ያንን ስላችሁ በቃ ስለእሷ የማትነግረን ጥቂት ነዋ..?››ብላችሁ ታስቡ ይሆናል፡፡አይደለም:: እንደውም በተቀራኒው የምነግራችሁ ከእሷ ታሪክ አንጻር ጥቂቱን ግን በእኛ በሰውኛ ልኬት ከጆሮአችን የመስማት አቅም በላይ ከአይኖቻችንም የማየት ጉልበት በላይ በሆነ መጠን ነግራችሆለው፡፡
ምክንቱም ይህቺ ፍቅሬ ከሰፈር ጎረምሳነት በአንዴ ስለዓለም መፅአዊ እጣ ሚያስብና ለዛም የሚሰራ የሚተጋ ሰው አድርጋ መልሳ ዳግመኛ የፈጠረቺኝ ሴት ነች፡፡እሷ ደፋርም ገራሚም ፍጡር ነች፡፡ ሁሉ ነገር የማድረግ አቅም እንዳላት አምናለው፡እንዴት አድርጌ የምታደርገው ነገር ሁሉ የምትለውን ሁሉ አምናታለው፡፡የማምናት ጅል ሆኜ አይደልም፡፡በአፍቃሪነቴም ዓየነ-ልቦናይ ታውሮም አይመስለኝም፤የምትሰራቸውን የእጆቾን ተአምራቶች በአይኖቼ ደጋግሜ ሳላየው ላለማመን አልችልም፡፡ ግን ደግሞ ሚስጥሯን ሁሉ ትነግረኛለች ብዬ አላስብም…ከእኔ የተደበቀ የሆነ ዕቅድ ያላት መስሎ ይሰማኛል ፡፡ቢሆንም ደፍሬ ጠይቄያት አላውቅም፡፡
ግን የምታወራው ስለአፈቀርካት ሴት ነው ወይ..? ካላችሁኝ አዎ ስለእሷው ነው፤ግን እንደምታውቋት አይነት ሴት ብቻ አይደለችም… መንፈስም ጭምር ነች፡፡ምን አይነት መንፈስ..?እሱን ወደ ፊት አስረዳችሆለው….
ይህቺን ሴት ያገኘዋት በተለየ አጋጣሚ ነው፡፡በህይወቴ የመጨረሸውን ሀዘን ባዘንኩበት ቀን …የመጨረሻውን እጦት ባጣውበት ቀን…ወደ ልቤ ደም የሚወስዱና የሚመልሱ ትላልቅ የደም ስሮች የተበጠሱ የመሰለኝ ቀን፡፡አዎ የዛን ቀን ነበር ያገኘዋት …፡፡እንዴት እጦቴን በተአምሮ መለሰችልኝ…ሀዘኔን በድንቅ ስራዋ ወደምስራች ቀየረችልኝ…የተበጣጠሱትን የልብን ደም ስሮች ቀጣጥላ ለሞት ከቆረጥኩበት ስሜት አውጥታ መኖርን እንድናፍቅ አደረገቺኝ እና በዛኑ ቅፅበት ይህቺን ሴት ደነዘዝኩላት….፡፡
ወዲያው ነበር እግሯ ስር ተንበርክኬ እንዳፈቀርኳት የነገርኳት..ይቺን ሴት ፍቅሬን እንደተቀበለች ነበር ትንፋሽ ሳልሰጣት እንድታገባኝ የጠየቀኳት፡፡አግቢኝ ስላት ቤት አልነበረኝም .አግቢኝ ስላት ስራ አልነበረኝም…አረ አግቢኝ ስላት የሀይስኩል ትምህርቴን እንኳን አልጨረስኩም…አግቢኝ ስላት የማግባት ዕቅድም አልነበረኝም….አግቢኝ ስላት ዕድሜዬ እንኳን 18 ሊደፍን ገና 3 ወራቶች ይቀሩት ነበር..
ይህ ሁሉ ቢሆንም ዳሩ እንድታገባኝ ስጠይቃት
-እንዳገባህ የጠየቅከኝ ውለታ ስለዋልኩልህ ነው ወይስ ስላፈቀርከኝ›ነበር ያለቺኝ
-ሁለቱም ምክንያት ነው፡፡-መለስኩላት
-ይሁን የመጣውትም አንተን ለማግባት ስለሆነ ተቀብዬሀለው ››አለቺኝ
-አልገባኝ
-ቀስ ብሎ ይገባሀል ..ለማንኛውም ጥያቄህን ተቀብያለው ፡፡አገባሀለው፡፡
መልሶን ስሰማ ደንግጬ ነበር..እሺታዋን ስሰማ ፈዝዤ ነበር፡፡አዎ እሺታዋን አልጠበቅኩም ነበር፡፡
-ግን ቆይ የመጣውት ስትይ ከየት ነው የመጣሽው.?
ከዛኛው አለም ….ላለፈት መቶ አመት እዚህ አልነበርኩም፡፡
-ያው እየቀለደች ነው ብዬ
‹ከዛ በፊትስ?፡›ጠየቅኳት
-ከዛ በፊት አንድ አራት ጊዜ ተመላልሺያለው፡፡ፈርዶብኝ ጀግና ወዳለው፡፡በዚህ አካባቢ ማለቴ በኢትዬጵያ ጀግና መኖሩን ከሰማው በርሬ ለመምጣት ቀናትን አላባክንም›
-ይገርማል…አሁን ታዲያ ማን ተገኝቶ ነው የመጣሺው.?›
-ነገርኩህ አንተን..
-እኔን …እኔ ታዲያ እንዴት ነው ከሌላ አለም የሚመጣልኝ ጀግና የሆንኩት?››ጠየቅኳት ያው በቀልድ ቅላፄ
-አይ እስከአሁን እንኳን ጀግና አይደለህም ….ግን ጀግና የሚሆን ልብ ይዘሀል፡፡በሺ አመት አንዴ የሚገኝ ጀግና ልብ…ስለዚህ አገባሀለው፡፡ግን አንድ አላማ አለኝ ያንን እንዳሳካ ታግዘኛለህ …እርግጥ ለእኔም ብቻ ሳይሆን ለአንተም ይጠቅማል፡፡
-አረ ግድ የለም ፡፡ለአንቺ ብቻ የሚጠቅምም ቢሆን ያልሺኝን ሁሉ አደርገዋለው›አልኳት ከልቤ እንደማደርገው በውስጤ እየማልኩ
የእለቱ ንግግራችንም ሆነ ጠቅላላ ታሪኩ በዚህ አልተቆጨም ሙሉውን ወደፊት አወራችሆለው …አሁን ከዚያች የህይወት አጋጣሚ አክለፍልፋ ወስዳ እሷ እጅ ወይም ልብ ላይ እስክትጥለኝ ድረስ ያሰለፍኩትን የእኔንና የቤተሰቤን ታሪክ ልክ እንደቅምሻ በሚቀጥሉት ክፍል አወራችሁና ስጨርስ ወደመነሻዬ እመልሳችሆለው፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_ሁለት
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
...ኢትዬጵያን በዩቶፐያ ፅንሰ ሀሳብ ዳግም መገንባት ከአያቴ የወረስኩት ህልሜ እና ዓላማዬ እንደሆነ ነግሬያችኃለው …ግን እንዴት አድርጌ ነው የማሳካው …?እንደማሳክው የማምነው ከራሴ በላይ በሚስቴ እምነት ስላለኝ ነው፡፡ሚስቴ …የዋናው የታሪኬ ማጠንጠኛ እሷ ነች፡፡እሷ ደግሞ መንፈስ ነች፡፡ገራሚ መንፈስ፡፡አስፈሪ መንፈስ፤ታሪካዊ መንፈስ፤አፍዛዥ መንፈስ…ሁሉን አድራጊ ፈላጭ ቆራጭ መንፈስ፡፡አዎ ስለእሷ የምነግራችሁ ነገር ቢኖር የደረስኩበትን እና ያወቅኩትን ብቻ ነው፡፡ያንን ስላችሁ በቃ ስለእሷ የማትነግረን ጥቂት ነዋ..?››ብላችሁ ታስቡ ይሆናል፡፡አይደለም:: እንደውም በተቀራኒው የምነግራችሁ ከእሷ ታሪክ አንጻር ጥቂቱን ግን በእኛ በሰውኛ ልኬት ከጆሮአችን የመስማት አቅም በላይ ከአይኖቻችንም የማየት ጉልበት በላይ በሆነ መጠን ነግራችሆለው፡፡
ምክንቱም ይህቺ ፍቅሬ ከሰፈር ጎረምሳነት በአንዴ ስለዓለም መፅአዊ እጣ ሚያስብና ለዛም የሚሰራ የሚተጋ ሰው አድርጋ መልሳ ዳግመኛ የፈጠረቺኝ ሴት ነች፡፡እሷ ደፋርም ገራሚም ፍጡር ነች፡፡ ሁሉ ነገር የማድረግ አቅም እንዳላት አምናለው፡እንዴት አድርጌ የምታደርገው ነገር ሁሉ የምትለውን ሁሉ አምናታለው፡፡የማምናት ጅል ሆኜ አይደልም፡፡በአፍቃሪነቴም ዓየነ-ልቦናይ ታውሮም አይመስለኝም፤የምትሰራቸውን የእጆቾን ተአምራቶች በአይኖቼ ደጋግሜ ሳላየው ላለማመን አልችልም፡፡ ግን ደግሞ ሚስጥሯን ሁሉ ትነግረኛለች ብዬ አላስብም…ከእኔ የተደበቀ የሆነ ዕቅድ ያላት መስሎ ይሰማኛል ፡፡ቢሆንም ደፍሬ ጠይቄያት አላውቅም፡፡
ግን የምታወራው ስለአፈቀርካት ሴት ነው ወይ..? ካላችሁኝ አዎ ስለእሷው ነው፤ግን እንደምታውቋት አይነት ሴት ብቻ አይደለችም… መንፈስም ጭምር ነች፡፡ምን አይነት መንፈስ..?እሱን ወደ ፊት አስረዳችሆለው….
ይህቺን ሴት ያገኘዋት በተለየ አጋጣሚ ነው፡፡በህይወቴ የመጨረሸውን ሀዘን ባዘንኩበት ቀን …የመጨረሻውን እጦት ባጣውበት ቀን…ወደ ልቤ ደም የሚወስዱና የሚመልሱ ትላልቅ የደም ስሮች የተበጠሱ የመሰለኝ ቀን፡፡አዎ የዛን ቀን ነበር ያገኘዋት …፡፡እንዴት እጦቴን በተአምሮ መለሰችልኝ…ሀዘኔን በድንቅ ስራዋ ወደምስራች ቀየረችልኝ…የተበጣጠሱትን የልብን ደም ስሮች ቀጣጥላ ለሞት ከቆረጥኩበት ስሜት አውጥታ መኖርን እንድናፍቅ አደረገቺኝ እና በዛኑ ቅፅበት ይህቺን ሴት ደነዘዝኩላት….፡፡
ወዲያው ነበር እግሯ ስር ተንበርክኬ እንዳፈቀርኳት የነገርኳት..ይቺን ሴት ፍቅሬን እንደተቀበለች ነበር ትንፋሽ ሳልሰጣት እንድታገባኝ የጠየቀኳት፡፡አግቢኝ ስላት ቤት አልነበረኝም .አግቢኝ ስላት ስራ አልነበረኝም…አረ አግቢኝ ስላት የሀይስኩል ትምህርቴን እንኳን አልጨረስኩም…አግቢኝ ስላት የማግባት ዕቅድም አልነበረኝም….አግቢኝ ስላት ዕድሜዬ እንኳን 18 ሊደፍን ገና 3 ወራቶች ይቀሩት ነበር..
ይህ ሁሉ ቢሆንም ዳሩ እንድታገባኝ ስጠይቃት
-እንዳገባህ የጠየቅከኝ ውለታ ስለዋልኩልህ ነው ወይስ ስላፈቀርከኝ›ነበር ያለቺኝ
-ሁለቱም ምክንያት ነው፡፡-መለስኩላት
-ይሁን የመጣውትም አንተን ለማግባት ስለሆነ ተቀብዬሀለው ››አለቺኝ
-አልገባኝ
-ቀስ ብሎ ይገባሀል ..ለማንኛውም ጥያቄህን ተቀብያለው ፡፡አገባሀለው፡፡
መልሶን ስሰማ ደንግጬ ነበር..እሺታዋን ስሰማ ፈዝዤ ነበር፡፡አዎ እሺታዋን አልጠበቅኩም ነበር፡፡
-ግን ቆይ የመጣውት ስትይ ከየት ነው የመጣሽው.?
ከዛኛው አለም ….ላለፈት መቶ አመት እዚህ አልነበርኩም፡፡
-ያው እየቀለደች ነው ብዬ
‹ከዛ በፊትስ?፡›ጠየቅኳት
-ከዛ በፊት አንድ አራት ጊዜ ተመላልሺያለው፡፡ፈርዶብኝ ጀግና ወዳለው፡፡በዚህ አካባቢ ማለቴ በኢትዬጵያ ጀግና መኖሩን ከሰማው በርሬ ለመምጣት ቀናትን አላባክንም›
-ይገርማል…አሁን ታዲያ ማን ተገኝቶ ነው የመጣሺው.?›
-ነገርኩህ አንተን..
-እኔን …እኔ ታዲያ እንዴት ነው ከሌላ አለም የሚመጣልኝ ጀግና የሆንኩት?››ጠየቅኳት ያው በቀልድ ቅላፄ
-አይ እስከአሁን እንኳን ጀግና አይደለህም ….ግን ጀግና የሚሆን ልብ ይዘሀል፡፡በሺ አመት አንዴ የሚገኝ ጀግና ልብ…ስለዚህ አገባሀለው፡፡ግን አንድ አላማ አለኝ ያንን እንዳሳካ ታግዘኛለህ …እርግጥ ለእኔም ብቻ ሳይሆን ለአንተም ይጠቅማል፡፡
-አረ ግድ የለም ፡፡ለአንቺ ብቻ የሚጠቅምም ቢሆን ያልሺኝን ሁሉ አደርገዋለው›አልኳት ከልቤ እንደማደርገው በውስጤ እየማልኩ
የእለቱ ንግግራችንም ሆነ ጠቅላላ ታሪኩ በዚህ አልተቆጨም ሙሉውን ወደፊት አወራችሆለው …አሁን ከዚያች የህይወት አጋጣሚ አክለፍልፋ ወስዳ እሷ እጅ ወይም ልብ ላይ እስክትጥለኝ ድረስ ያሰለፍኩትን የእኔንና የቤተሰቤን ታሪክ ልክ እንደቅምሻ በሚቀጥሉት ክፍል አወራችሁና ስጨርስ ወደመነሻዬ እመልሳችሆለው፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3
#አስራ_ሶስተኛው_ፍቅር !
እንዴት ዋላችሁ ህዝቤ? ሁሉ ፒስ ነው ወይ? በቃ ምንም እንደሌለብህ ሐገርህን ለአክቲቪስት ጥለህ ለጥ ትልልኛለህ ኣ? ለነገሩ ለምን ይዋሻል እኔም በጥልቅ እንቅልፍ ውስጥ ሆኜ ነው ያደርኩት! ህልሜን ሁሉ በሪሞት እየቀያየርኩ ሳይ ነበር። “ደሃ በህልሙ ቅቤ ባይጠጣ ኖሮ” .... አሉ አበው (መቼስ የኛ ሐገር አበውና የኛ ሐገር አክቲቪስት ማይለው የለም) የምር ግን እኛ ድሆች በህልማችን ቅቤ ባንጠጣ ኖሮኮ ...... ያው አልጠጣንም ነዋ ምናባታችን እናመጣለን!😄
እና በተረፈ ሁሉ አማን ነው ወይ? እኔ ለአስራሶስተኛ ግዜ ፍቅር ይዞኝ መከራዬን ሳይ ነው የከረምኩት። ያው እንደህንድ አክተር ፍቅር ሚያጠቃኝ ነገር አለ ኣ?? .... ልቤ ተላላ ነገር ነው። ከአንድ ሴት ጋር ተግባብቼ ትንሽ ከተጨዋወትኩ ጠላታችሁ ቅይር ይበል ቅይር እላለሁ። ፈገግታዋ ልቤን ትርክክ ያደርገዋል። ሰባት ግዜ የሰማሁትን ቀልድ ስትነግረኝ እየተንፈራፈርኩ እስቃለሁ። አረ ስተኛ ራሱ በህልሜ አያታለሁ። ይኸው እኛ መስሪያቤት የምትሰራው ትርሲትም ሰው ነው ብላ ብትቀርበኝ አፍቅሪያት አረፍኩት! ባፈቀርኳት ማግስትም የናቲ ማንን «የመጀመሪያዬ ነው ሰው ስወድ አምርሬ» የሚለውን ዘፈን ጋበዝኳት! (በርግጥ «አስራሶስተኛዬ ነው ሰው ስወድ አምርሬ» አይባል ነገር ችግር ሆኖብኝ እንጂ የመጀመሪያዬንኳ አልነበረም!)
ከትርሲት ጋር ብዙ ግዜ አብረን ብንሰራም በፍቅር አይን አይቻት አላውቅም ነበር። ባለፈው የአንድ የስራ ባልደረባችን እናት ድንገት አረፉና ማታ ከመስሪያ ቤታችን ሰዎች ጋር ለቅሶ ቤት ሄድን።
ድንኳኗ በሰው ተሞልታለች። ወጣቶቹ በካርታ ቁማር እየተጫወቱ ድንኳኑን ካሲኖ አስመስለውታል። በሩ አካባቢ ቁጭ አልን። ያው እኔ አርፌ አልቀመጥም አይደል አይኔን ማንከራተት ጀመርኩ። እናንተ!! ሰዉ ይሄን ንፍሮ ይዝቀው የለ እንዴ? ጥግ አካባቢ ያለው ሰውዬማ ንፍሮውን ከሰሃኑ እየዘገነ በሁለቱም የጃኬቱ ኪስ ውስጥ ጠቅጥቆ ብድግ ሲል ቦንብ የታጠቀ ነበር የመሰለኝ።
ትንሽ እንደቆየን አንዱ ሰካራም ገድገድ እያለ ከውጪ ገብቶ ወደኛ ጠጋ አለና
«ጋሽ ለገሰ ሞቱንዴ?» አለን
«አይ የጋሽ ለገሰ ለቅሶ አይደለም» አልነው።
«አሃ አሃ! ለካ እሳቸው አምና ሞተዋል። ፊት ለፊት ያለው ግቢ የሚኖሩት መምህር ጥበቡ ነዋ የሞቱት» ሲል
«አረ ኔ አለሁ ምን ያሟርትብኛል ይሄ» አሉ ከኋላችን የተቀመጡ ሰውዬ።
በወሬው የተሰላቸው ሰካራም «በቃ ማንም ይሁን ማን የሆነ ሰው ሞቷል። ዋናው ጥያቄ እራት ሰአት አልፏል ወይ? የሚለው ነው» ሲለን ሳቃችንን እንደምንም ተቆጣጥረን ጠጋ ብለን አጠገባችን አስቀመጥነው።
ትንሽ ቆይቶ ራት ቀረበ። ፒፕሉ የተቆረጠውን እንጀራ እንደቆሎ ዘገነው። ሰውዬውም እንጀራውን እንደአንሶላ ደራርቦ ሰሃኑ ላይ ካነጠፈ በኋላ ወጥ አስደርጎ ከራሱ ጋር እየተሻማ ሁለት ሶስቴ ጎረሰና ረሃቡ መለስ ሲልለት ወደኔ ዞሮ
«ምን ሆነው ሞቱ ግን?» አለኝ
«መኪና ገጭቷቸው መሰለኝ» አልኩት። ከልቡ አልሰማኝም እንጀራውን እየጠቀለለ
«እና ተረፉ?» አለኝ
«እንዴት ተረፉ?» አልኩት ግራ ገብቶኝ
«ውይ የኔ ነገር ሞተዋል ለካ ... ባክህ ስሞትልህ አንዴ ላጉርስህ» አለኝ እንጀራውን ወደአፌ እያስጠጋ
«አይ በልቻለሁ ይቅርብኝ» ስለው «ይሁና» ብሎ ምግቡን ጨርሶ ከበላ በኋላ ከመቀመጫው ተነሳና ባርኔጣውን ከፍ አርጎ
«ያመት አመት ሰው ይበለን። መጥተን አንጣችሁ» ብሎ ወጣ።
በሰውዬው ሁኔታ እየሳቅን ሳለ ነው ትርሲት ከተፍ ያለችው! እግዚኦ ውበት! እግዞኦ ቁንጅና! ሰው ለቅሶ ቤት ለመምጣት እንዲህ ይሽቀረቀራል በናታችሁ? መስሪያ ቤት የማውቃት ትርሲት አትመስልም። ያቺን ትርሲት እዛው መስሪያቤት አወላልቃ ጥላ አዲስ ታጥቦ የተተኮሰ ቆዳ ለብሳ የመጣች ነው ምትመስለው። መስሪያ ቤት ጠቅልላ የምትቋጥረው ፀጉሯ ራሱ ተለቆ ትከሻዋ ላይ እየተዘናፈለ ልዩ ውበት ሰጥቷታል (ያው የራሷ መሆንና አለመሆኑ በሂደት ይጣራል) አንገቷን እንዳቀረቀረች ወደድንኳኑ ገብታ ተቀመጠች።
«እቺን ልጅ እስካሁን እንዴት አላፈቀርኳትም» አልኩ በልቤ። አንዳንዴኮ አይጋርድባችሁ ወንድሞቼ!
ከለቅሶ ቤቱ ስትወጣ ተከትያት ወጥቼ ሸኘኋት። በቃ ከዛን ቀን ወዲህ ተቀራረብን። በየቀኑ መገናኘት ጀመርን። ሻይ ቡናም ተባባልን። አረ እራትም በልተናል። በርግጥ እራት በላን ከምል ማጅራት ተመታሁ ብል ይቀለኛል።
ማውቀው ቤት አለ ብላኝ የከተማዋ ቱጃሮች ሚዝናኑበት ባር እየጎተተች ይዛኝ ሄደች።
የባሩ ዋቴ የጀመረው ገና ስንገባ ነው። ጋርዱ ጠብ እርግፍ ብሎ እጅ ነስቶ በር ከፍቶ በትህትና ሲያስገባኝ ነው መፍራት የጀመርኩት። ልክ ገብተን እንደተቀመጥን አስተናጋጇ ወርቃማ ፍሬም የሚመስል ሜኑ አመጣች። ትርሲት ልክ ማትሪክ እንደሚፈተን ሰው ሜኑውን በጥሞና ስታነብ ቆይታ የሆነ ምግብ አዘዘች። እኔም አይኖቿን እያየሁ ፈዝዤ እሷ ያዘዘችውን አምጪልኝ አልኩ። ከአፍታ ቆይታ በኋላ በሁለት ሰሃን ባቄላ ቲማቲም ምናምን ቀረበልን። ስታርተር መስሎኝ ዋናውን ምግብ ስጠብቅ ቀረ። ቢቸግረኝ ባቄላዬን በላሁና ሚጠጣ ለማዘዝ ቀና ስል አስተናጋጇ አጠገቤ ደርሳ «ምን ይጨመር የኔ ጌታ» አለችኝ። አስተናጋጇ ቤቱን ለማየትም እድል አትሰጥም። ቀና ባልኩ ቁጥር ተፈናጥራ እየመጣች «ምን ይጨመር» ስትለኝ ነው ያመሸችው። ዋይን በግላስ አዘዝኩ። ትርሲትም ነጭ ዋይን አለች። ብቻ ላሳጥረውና ቢሉ መጥቶ የወር ደሞዜን ዱቅ አርጌ ያን ምሽት እንዳኮረፍኩ ብዙም ሳናወራ ተለያየን።
ትርሲት ሁሉ ነገሯ ጥሩ ነው። እሷን ማፍቀሬም የሚካድ አይደለም። ግን ችግር አለ! በጣም ጨምላቃ ነች! ፍላጎቷ ከኔ አቅም በላይ ነው። ፋይፍ ስታር ሆቴል ካልሄደች እህል አይወርድላትም። አራት ዲጂት ያለው ቢል ካልመጣ የተዝናናች አይመስላትም። ሳስበው የቀድሞ ቦይፍሬንዷ ከሜቴክ ጋር ግንኙነት ሳይኖረው አይቀርም። መርከብ የበላ እንጂ እንደኔ አይነት ሚጢጢ ደሞዝ ሚበላ ሰው አይችላትም። በቃ ሁሉ ነገሯ ወጪ አለው። አንዳንዴማ የነዳጅ ጉድጓድ ያለኝ ሁሉ ሳይመስላት አይቀርም።
ፍቅርኮ ደስ የሚለው እንደአማርኛ ፊልም ቆሎ እየቆረጠሙ በሻይ እያወራረዱ፣ በቆሎ እየጋጡ ወክ ሲያደርጉ ምናምን ነው። እቺኮ ከእንትን ባር ወደእንትና ላውንጅ ነው። ከእንትና ላውንጅ ወደእንትና ስፓ ነው። ሁሉ ነገሯ ኤክስፔንሲቭ!
ቁጭ ብዬ የወደፊት ሂወቴን ከሷ ጋር ማሰብ ጀመርኩ። ምርጫዬ ሁለት ነው። ወይ ባንክ መዝረፍ ወይ ፍቅር ምናምን ሚባለውን ነገር እርግፍ አርጎ መተው! ድህነቴን እንደዘንድሮ ጠልቼው አላውቅም። ሟቹ ጠቅላያችን “ትልቁ ጠላታችን ድህነት ነው” ያሉት ራሱ እንደኔ አይነቷ ገጥማቸው ሳይሆን አይቀርም! .... ትርሲትን መተው ከባድ ነው። ባንክ መዝረፉም ቀላል አይደለም። ይሄኔኮ «ምን ጣጣ አለው ሰው አስራስምንት ባንክ ይዘርፍ የለንዴ» ትዪ ይሆናል አዳሜ። (ወዳጄ አንድ ቡድንኮ ከሶስት ግዜ በላይ ባንክ ከዘረፈ ከስተመር ነው እንጂ ዘራፊ አይባልም። እንደውም ባንኩ ቆጥሮ አስፈርሞ “አትጥፋ በሰላም ግባ” ምናምን ብሎ ነው ሚሸኘው)
በቃ ተሸበለልኩ! ነፋስ ሆንኩ! በኪሎሜትር እራቅኋት!
«አቅምን አውቆ መኖር ጥሩ ነው» ብሎ የዘፈነው ሰዉዬ ማን ነበር? ....ብቻ ማንም ይሁን ማን አፈላልጋችሁ የክብር ዶክትሬት ስጡልኝ!😂
🔘ዘውዳለም ታደሠ🔘
እንዴት ዋላችሁ ህዝቤ? ሁሉ ፒስ ነው ወይ? በቃ ምንም እንደሌለብህ ሐገርህን ለአክቲቪስት ጥለህ ለጥ ትልልኛለህ ኣ? ለነገሩ ለምን ይዋሻል እኔም በጥልቅ እንቅልፍ ውስጥ ሆኜ ነው ያደርኩት! ህልሜን ሁሉ በሪሞት እየቀያየርኩ ሳይ ነበር። “ደሃ በህልሙ ቅቤ ባይጠጣ ኖሮ” .... አሉ አበው (መቼስ የኛ ሐገር አበውና የኛ ሐገር አክቲቪስት ማይለው የለም) የምር ግን እኛ ድሆች በህልማችን ቅቤ ባንጠጣ ኖሮኮ ...... ያው አልጠጣንም ነዋ ምናባታችን እናመጣለን!😄
እና በተረፈ ሁሉ አማን ነው ወይ? እኔ ለአስራሶስተኛ ግዜ ፍቅር ይዞኝ መከራዬን ሳይ ነው የከረምኩት። ያው እንደህንድ አክተር ፍቅር ሚያጠቃኝ ነገር አለ ኣ?? .... ልቤ ተላላ ነገር ነው። ከአንድ ሴት ጋር ተግባብቼ ትንሽ ከተጨዋወትኩ ጠላታችሁ ቅይር ይበል ቅይር እላለሁ። ፈገግታዋ ልቤን ትርክክ ያደርገዋል። ሰባት ግዜ የሰማሁትን ቀልድ ስትነግረኝ እየተንፈራፈርኩ እስቃለሁ። አረ ስተኛ ራሱ በህልሜ አያታለሁ። ይኸው እኛ መስሪያቤት የምትሰራው ትርሲትም ሰው ነው ብላ ብትቀርበኝ አፍቅሪያት አረፍኩት! ባፈቀርኳት ማግስትም የናቲ ማንን «የመጀመሪያዬ ነው ሰው ስወድ አምርሬ» የሚለውን ዘፈን ጋበዝኳት! (በርግጥ «አስራሶስተኛዬ ነው ሰው ስወድ አምርሬ» አይባል ነገር ችግር ሆኖብኝ እንጂ የመጀመሪያዬንኳ አልነበረም!)
ከትርሲት ጋር ብዙ ግዜ አብረን ብንሰራም በፍቅር አይን አይቻት አላውቅም ነበር። ባለፈው የአንድ የስራ ባልደረባችን እናት ድንገት አረፉና ማታ ከመስሪያ ቤታችን ሰዎች ጋር ለቅሶ ቤት ሄድን።
ድንኳኗ በሰው ተሞልታለች። ወጣቶቹ በካርታ ቁማር እየተጫወቱ ድንኳኑን ካሲኖ አስመስለውታል። በሩ አካባቢ ቁጭ አልን። ያው እኔ አርፌ አልቀመጥም አይደል አይኔን ማንከራተት ጀመርኩ። እናንተ!! ሰዉ ይሄን ንፍሮ ይዝቀው የለ እንዴ? ጥግ አካባቢ ያለው ሰውዬማ ንፍሮውን ከሰሃኑ እየዘገነ በሁለቱም የጃኬቱ ኪስ ውስጥ ጠቅጥቆ ብድግ ሲል ቦንብ የታጠቀ ነበር የመሰለኝ።
ትንሽ እንደቆየን አንዱ ሰካራም ገድገድ እያለ ከውጪ ገብቶ ወደኛ ጠጋ አለና
«ጋሽ ለገሰ ሞቱንዴ?» አለን
«አይ የጋሽ ለገሰ ለቅሶ አይደለም» አልነው።
«አሃ አሃ! ለካ እሳቸው አምና ሞተዋል። ፊት ለፊት ያለው ግቢ የሚኖሩት መምህር ጥበቡ ነዋ የሞቱት» ሲል
«አረ ኔ አለሁ ምን ያሟርትብኛል ይሄ» አሉ ከኋላችን የተቀመጡ ሰውዬ።
በወሬው የተሰላቸው ሰካራም «በቃ ማንም ይሁን ማን የሆነ ሰው ሞቷል። ዋናው ጥያቄ እራት ሰአት አልፏል ወይ? የሚለው ነው» ሲለን ሳቃችንን እንደምንም ተቆጣጥረን ጠጋ ብለን አጠገባችን አስቀመጥነው።
ትንሽ ቆይቶ ራት ቀረበ። ፒፕሉ የተቆረጠውን እንጀራ እንደቆሎ ዘገነው። ሰውዬውም እንጀራውን እንደአንሶላ ደራርቦ ሰሃኑ ላይ ካነጠፈ በኋላ ወጥ አስደርጎ ከራሱ ጋር እየተሻማ ሁለት ሶስቴ ጎረሰና ረሃቡ መለስ ሲልለት ወደኔ ዞሮ
«ምን ሆነው ሞቱ ግን?» አለኝ
«መኪና ገጭቷቸው መሰለኝ» አልኩት። ከልቡ አልሰማኝም እንጀራውን እየጠቀለለ
«እና ተረፉ?» አለኝ
«እንዴት ተረፉ?» አልኩት ግራ ገብቶኝ
«ውይ የኔ ነገር ሞተዋል ለካ ... ባክህ ስሞትልህ አንዴ ላጉርስህ» አለኝ እንጀራውን ወደአፌ እያስጠጋ
«አይ በልቻለሁ ይቅርብኝ» ስለው «ይሁና» ብሎ ምግቡን ጨርሶ ከበላ በኋላ ከመቀመጫው ተነሳና ባርኔጣውን ከፍ አርጎ
«ያመት አመት ሰው ይበለን። መጥተን አንጣችሁ» ብሎ ወጣ።
በሰውዬው ሁኔታ እየሳቅን ሳለ ነው ትርሲት ከተፍ ያለችው! እግዚኦ ውበት! እግዞኦ ቁንጅና! ሰው ለቅሶ ቤት ለመምጣት እንዲህ ይሽቀረቀራል በናታችሁ? መስሪያ ቤት የማውቃት ትርሲት አትመስልም። ያቺን ትርሲት እዛው መስሪያቤት አወላልቃ ጥላ አዲስ ታጥቦ የተተኮሰ ቆዳ ለብሳ የመጣች ነው ምትመስለው። መስሪያ ቤት ጠቅልላ የምትቋጥረው ፀጉሯ ራሱ ተለቆ ትከሻዋ ላይ እየተዘናፈለ ልዩ ውበት ሰጥቷታል (ያው የራሷ መሆንና አለመሆኑ በሂደት ይጣራል) አንገቷን እንዳቀረቀረች ወደድንኳኑ ገብታ ተቀመጠች።
«እቺን ልጅ እስካሁን እንዴት አላፈቀርኳትም» አልኩ በልቤ። አንዳንዴኮ አይጋርድባችሁ ወንድሞቼ!
ከለቅሶ ቤቱ ስትወጣ ተከትያት ወጥቼ ሸኘኋት። በቃ ከዛን ቀን ወዲህ ተቀራረብን። በየቀኑ መገናኘት ጀመርን። ሻይ ቡናም ተባባልን። አረ እራትም በልተናል። በርግጥ እራት በላን ከምል ማጅራት ተመታሁ ብል ይቀለኛል።
ማውቀው ቤት አለ ብላኝ የከተማዋ ቱጃሮች ሚዝናኑበት ባር እየጎተተች ይዛኝ ሄደች።
የባሩ ዋቴ የጀመረው ገና ስንገባ ነው። ጋርዱ ጠብ እርግፍ ብሎ እጅ ነስቶ በር ከፍቶ በትህትና ሲያስገባኝ ነው መፍራት የጀመርኩት። ልክ ገብተን እንደተቀመጥን አስተናጋጇ ወርቃማ ፍሬም የሚመስል ሜኑ አመጣች። ትርሲት ልክ ማትሪክ እንደሚፈተን ሰው ሜኑውን በጥሞና ስታነብ ቆይታ የሆነ ምግብ አዘዘች። እኔም አይኖቿን እያየሁ ፈዝዤ እሷ ያዘዘችውን አምጪልኝ አልኩ። ከአፍታ ቆይታ በኋላ በሁለት ሰሃን ባቄላ ቲማቲም ምናምን ቀረበልን። ስታርተር መስሎኝ ዋናውን ምግብ ስጠብቅ ቀረ። ቢቸግረኝ ባቄላዬን በላሁና ሚጠጣ ለማዘዝ ቀና ስል አስተናጋጇ አጠገቤ ደርሳ «ምን ይጨመር የኔ ጌታ» አለችኝ። አስተናጋጇ ቤቱን ለማየትም እድል አትሰጥም። ቀና ባልኩ ቁጥር ተፈናጥራ እየመጣች «ምን ይጨመር» ስትለኝ ነው ያመሸችው። ዋይን በግላስ አዘዝኩ። ትርሲትም ነጭ ዋይን አለች። ብቻ ላሳጥረውና ቢሉ መጥቶ የወር ደሞዜን ዱቅ አርጌ ያን ምሽት እንዳኮረፍኩ ብዙም ሳናወራ ተለያየን።
ትርሲት ሁሉ ነገሯ ጥሩ ነው። እሷን ማፍቀሬም የሚካድ አይደለም። ግን ችግር አለ! በጣም ጨምላቃ ነች! ፍላጎቷ ከኔ አቅም በላይ ነው። ፋይፍ ስታር ሆቴል ካልሄደች እህል አይወርድላትም። አራት ዲጂት ያለው ቢል ካልመጣ የተዝናናች አይመስላትም። ሳስበው የቀድሞ ቦይፍሬንዷ ከሜቴክ ጋር ግንኙነት ሳይኖረው አይቀርም። መርከብ የበላ እንጂ እንደኔ አይነት ሚጢጢ ደሞዝ ሚበላ ሰው አይችላትም። በቃ ሁሉ ነገሯ ወጪ አለው። አንዳንዴማ የነዳጅ ጉድጓድ ያለኝ ሁሉ ሳይመስላት አይቀርም።
ፍቅርኮ ደስ የሚለው እንደአማርኛ ፊልም ቆሎ እየቆረጠሙ በሻይ እያወራረዱ፣ በቆሎ እየጋጡ ወክ ሲያደርጉ ምናምን ነው። እቺኮ ከእንትን ባር ወደእንትና ላውንጅ ነው። ከእንትና ላውንጅ ወደእንትና ስፓ ነው። ሁሉ ነገሯ ኤክስፔንሲቭ!
ቁጭ ብዬ የወደፊት ሂወቴን ከሷ ጋር ማሰብ ጀመርኩ። ምርጫዬ ሁለት ነው። ወይ ባንክ መዝረፍ ወይ ፍቅር ምናምን ሚባለውን ነገር እርግፍ አርጎ መተው! ድህነቴን እንደዘንድሮ ጠልቼው አላውቅም። ሟቹ ጠቅላያችን “ትልቁ ጠላታችን ድህነት ነው” ያሉት ራሱ እንደኔ አይነቷ ገጥማቸው ሳይሆን አይቀርም! .... ትርሲትን መተው ከባድ ነው። ባንክ መዝረፉም ቀላል አይደለም። ይሄኔኮ «ምን ጣጣ አለው ሰው አስራስምንት ባንክ ይዘርፍ የለንዴ» ትዪ ይሆናል አዳሜ። (ወዳጄ አንድ ቡድንኮ ከሶስት ግዜ በላይ ባንክ ከዘረፈ ከስተመር ነው እንጂ ዘራፊ አይባልም። እንደውም ባንኩ ቆጥሮ አስፈርሞ “አትጥፋ በሰላም ግባ” ምናምን ብሎ ነው ሚሸኘው)
በቃ ተሸበለልኩ! ነፋስ ሆንኩ! በኪሎሜትር እራቅኋት!
«አቅምን አውቆ መኖር ጥሩ ነው» ብሎ የዘፈነው ሰዉዬ ማን ነበር? ....ብቻ ማንም ይሁን ማን አፈላልጋችሁ የክብር ዶክትሬት ስጡልኝ!😂
🔘ዘውዳለም ታደሠ🔘
👍5😁1