አትሮኖስ
286K subscribers
121 photos
3 videos
41 files
572 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
ጥብቅ አድርጋ አቀፈችኝ። ጥብቅ ! አውቄያለሁ ሙና እየተለየችኝ ነው። ተነሳች .. ቦርሳዋን አነሳች ..
ቆም ብላ አይታኝ ወደ በሩ አመራች፤ ከፍታ ስትወጣ አላየኋትም።
እስከ ምሳ ሰዓት ከተቀመጥኩበት ሳልንቀሳቀስ ቁጭ ብዬ፣ ምንም ሳላስብ፣ ምንም ሳላይ ምንም ሆኜ ቆየሁ። የሆነ የመሬት ስበት የሌለበት ሕዋ ላይ እንደመንሳፈፍ ዓይነት ስሜት።
“ቻው ሙና” አልኩ ቁርስ ሰዓት ላይ የወጣችውን ልጅ ምሳ ሰዓት ላይ …. ቻው !
በሕዋ ላይ እየተንሳፈፍኩ ሥራ እሄዳለሁ፣ እመጣለሁ፤ እሄዳለሁ፣ እመጣለሁ … ከሙና ጋር ከተለያየን
2.3.45.67...
ወራት! “ግን ምክንያቱ ያለያይ ነበር እንዴ ?” እላለሁ አንዳንዴ። ሙና ቢያንስ የእኔ ችግር አለመሆኑን አውቃ፣ “እንዴት ሆንክ አይዞህ” አትለኝም እንዴ ? እላለሁ። ቅዳሜ ሁልጊዜ
የምትመጣ ይመስለኛል። ሁልጊዜ ከመኝታ ቤት ስወጣ ሳሎን ተቀምጣ የማገኛት ይመስለኛል። ሙና አለመደወሏ ይገርመኛል። ለድፍን ሰባት ወራት ስልኬ ሲጮህ ሙና እንደምትሆን እርግጠኛ ሆኜ አነሳው ነበር። ሙና ግን ተወችኝ !! (ተወችኝ ቃሉ እንዴት ያማል) ስልኳን ከሄደች ከሳምንቱ ጀምሮ እሞክር ነበር፤ አይሰራም ቁጥር ቀይራ ይሆናል።

ከሙና ጋር ከተለያየን ከዓመት ከምናምን በኋላ ሃኒባል እንዲህ አለኝ፣ “አብርሽ ከሌላ ሰው ሰምተህ ከምታዝን ራሴ ልንገርህ ብዬ ነው”

“ምንድን ነው”

ሙና ልታገባ ነው። ነገ እሁድ ነው ሰርጓ። አልደነገጥኩ፣ አልተከፋሁ፣ አልተደሰትኩ፣ አላዘንኩ !!
ድንዙዝ !!
እና ይሄ ምኑ ያሳዝናል” አልኩት ሃኒባልን።
( እ ? ሙና እኮ ነው ያልኩህ” አለ በግርምት እያየኝ።
“አይገርምም” ደገምኩለት ! የፍቅረኛ ሌላ ሰው ማግባት የመጨረሻው ጭካኔ የሚመስላቸው የመጨረሻ የዋህ ሰዎች አሉ። በፍቅር ውስጥ የመጨረሻው ህቅታ .. ጀርባን መስጠት ነው። ሙና ጀርባዋን ሰጥታኛለች። በእርግጥ እውነት አላት፤ ሙሉ ለሙሉ እኔ ችግር ውስጥ ነኝ። ሙና ደግሞ
ሰው ናት። ስለዚህ መሟዘዙ እድሜንም ስሜትንም ማባከን ነው፤ ደግ ሄደች ! እንኳንም ለቁም ነገር አበቃት። በቃ! ሙና ድል ባለ ሰርግ አገባች። የሰርጓ ቀን እዚህ ብሔራዊ መናፈሻ ውስጥ ተቀምጬ ዝም ብዬ ያንን የድንጋይ አንበሳ ሳየው ዋልኩ። “አንበሳው አንበሳ ባይመስልም የበላው ብር አንበሳ
ያስመስለዋል” አሉ አሉ ንጉሡ። ወንድነታችን ወንድ ባይሆንም ወንድ ለመምሰል ያቃጠልነው
ጊዜ ወንድ ያስመስለናል። ማሕበረሰቡ የከፈለልን የሞራልና የባሕል ዋጋ ወንድ ያደርገናል ... ቱ ! ቀፋፊ ቀን !! በሕይወት ውስጥ እንዲህ አፈር ድቤ በሚያስበላ ሽንፈት ያለህን ሁሉ ተነጥቀህ ባዶህን ሐውልት ሆነህ ሐውልት ፊት የምትቀመጥበት ጊዜ አለ። ያው ሐውልቱም የራሱ ታሪክ አለው፤ አገር የሚያውቀው። አንተም ታሪክ አለህ ማንም የማያውቀው፤ ብቻህን የሚያንገበግብህ። የእኔና የዚህ
የአንበሳ ሐውልት አንድነታችን ሁለታችንም የምንመስለውን አለመሆናችን ነው። እሱም አንበሳ፣ እኔም ወንድ አይደለሁም፤ መምሰል ብቻ።

አንዲት የሙና ጓደኛ አለች ሔዋን የምትባል። ከጥቁረቷ ብዛት የሙና ጥላ የምትመስል። ጀበና ሔዋን ጎን ቢቀመጥ ጠይም ይባላል። ጥቅጥቅ ያለ ጨለማ የመሰለች። ድሮ እንኳን ብዙም አልቀርባትም ነበር፤ ከሙና ጋር ከተለያየን ጀምሮ ግን ሙና ስትናፍቀኝ አገኛታለሁ። እንዲሁ የጋራ ጉዳያችን ሙና ሆና።

“ሙና ደህና ነች ?” እላታለሁ።

“ደህና ነች”

“ፀሐይ ሲመታት ራሷን ያማት ነበር፤ አሁን እንዴት ነች ?”

“ደህና ናት ! ባሏ መኪና ገዝቶላታል፤ ፀሐይ የት ያገኛታል ብለህ ሃሃሃሃሃሃ

“ማንስትሬሽን ላይ ስትሆን በጣም ነበር የሚያማት አሁን እንዴት ሆና ይሆን ?”
አይ አብርሽ ! እሱማ ያው በየወሩ ነው አይቀየር ነገር፤ ስትወልድ ይተዋል ይባላል ባይ ዘ ዌይ
ሙና እርጉዝ ናት !” ልቤ ላይ የሆነ ነገር ሲሰካ ይሰማኛል። አገባች ሲባል ምንም ያልተሰማኝን፣ ልከ
እርምህን አውጣ ዓይነት መርዶ ይመስል ይሄንኛው አመመኝ፤ በጣም አመመኝ።

ከመቀሌ ወደዚህ ለመምጣት ቅያሬ ጠይቃ ነበር ተሳክቶላት ይሆን ?”

“ጠይቃ ነበር እንዴ ? እኔ ይሄንን አላወቅኩም ... አሁን ግን ሥራ አቁማለችኮ” አለችኝ በግርምት
(ምን አስገረማት)። በቃ ስለሙና ጥግብ እስከምል እጠይቃታለሁ፤ ሳትሰለች ታወራኛለች። መተንፈሻዬ
ሔዋን። በጣም ተቀራረብን፤ ቤቷ ሁሉ ወስዳኝ ቡና ታፈላልኛለች። መቼም መድረሻ ቢስ ሆኛለሁ።
ሙና ከሄደች በኋላ ለጎተተኝ የምጎተት ከርታታ ዘባተሎ ነገር ... የት ነበርክ ብባል እዚህ የማልል
የቱንም ያህል ጥብርር ያላችሁ ብትሆኑ፣ ሰው ለዓይኑ የሚናፍቃችሁ እንኳን ብትሆኑ፣ የሆነ ጊዜ አለ
እንደምናምንቴ የትም የምትገኙበት፣ ምነው በዛህ የምትባሉበት ...

አንድ ቀን ታዲያ ሔዋን ቤት ሄደን ከተደረደሩት ሲዲዎች አንዱ ላይ ዓይኔ አረፈ። የሙና የሰርግ
ቪዲዮ ! እንድትከፍትልኝ ሔዋንን ጠየቅኳት። አንገራግራ ተለምና በመከራ ከፈተችልኝ። ሙናዬ የኔ
ቆንጆ እንዴት ነው ያማረችው በእግዚአብሔር ! ባሏም ቆንጆ ኃብታም ነው። እንደኔ ኮሳሳ ሳይሆን የሆነ ግርማ ሞገስ ያለው፤ በጣም ነው የሚመጣጠኑት ! ቀናሁ፣ አደገኛ የበታችነት ስሜት ደቆሰኝ።
ቪዲዮውን እያየሁ ነው፤ ባሏ ለቤተዘመዱ ዲስኩር እያሰማ ሙና ከጎኑ ቆማ በእፍረት ትሽኮረመማለች
(ስትሽኮረመም ስታምር !)

እና የሙና ባል በኩራት እንዲህ አለ፣ (እጁን የሙና ትከሻ ላይ ጣል አድርጎ ... የእኔ ትከሻ ላይ እጁ
ያረፈ ያህል ከበደኝ)

ከሙና ጋር የዛሬ (ሦስት ዓመት) ፍቅር ስንጀምር፣ ለእኔ የከፈለችውን መስዋትነት ባትከፍል ኑሮ ለዚህቀን ባልበቃን ነበር። እኔ መቀሌ፣ እሷ አዲስ አበባ ሆነን((((ለእኔ ስትል ቅያሬ ጠይቃ መቀሌ ድረስ መጣች))))። የፍቅር ጀግና ናት ሙንዬ” ... ታዳሚው አጨበጨበ ቿቿቿቿቿቿቿቿቿቿቿቿ
ቿቿቿቿቿቿቿቿቿቿቿቿቿቿቿ

ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ አብርሾ ሞኙ ሰው አማኙ..እንደ እብድ ነው የሳቅኩት።
አስታወስኩ…አንድ ጊዜ መቀሌ ሄጄ የሙና ቤት አከራይ፣ “ደህና ዋልክ አክሊሉ” አሉኝ። ወደ እርሳቸው ስዞር፣ “የኔ ነገር ያንዱን ስም ከአንዱ ማጋጨት” ብለው ሳቁ። የሙና ባል አክሊሉ ነው ሥሙ!

ተቀበል አዝማሪ ...

ኧረ ሙና ሙና ሙና አቀበቲቱ፣
ስቃ ገደለችው ወንዱን ልጅ ሴቲቱ!
አሁን ሰሜን ደቡብ ምን ያሰኘዋል ሰው፣
አሁን ቆላ ደጋ ምን ያሰኘዋል ሰው፣
እንዴት ዞሮ ማያ አንገቱን ያጣል ሰው፣
እንዴት ማስተዋያ ዓይኑንስ ያጣል ሰው፣
ያጣል ሰው

ያጣል ሰው ሚሊየን ጊዜ እስከ ምፅዓት ድገመው!

አንድ ሰው አራት የሚሆንበት ምናይነት ዘመን መጣ ?! ይሄ የሰርግ ቪዲዮ አይደለም። ስምንተኛው ሺ በራችንን እያንኳኳ መሆኑን የሚያረዳ “ዶክመንተሪ” እንጂ !! ቱ ! አፈርኩ እግዚአብሔርን - አፈርኩ! ሐፍረቱ አሸማቀቀኝ። ቅናት ሳይሆን ሐፍረት ! የዛሬ ሦስት አመት ማለት እኮ ከሙና ጋር በፍቅር
ያበድንበት ጊዜ ነበር። አንዲት የባንክ ሰራተኛ ከመቀሌ አዲስ አበባ በአውሮፕላን ስትመላለስ ብሩ ከየት መጣ እንዴት አላልኩም ... ! አፈርኩ በራሴ ! አንዲት የባንክ ሰራተኛ የወርቅ ሃብል ገዝታ ስትሰጠኝ እንዴት ብሩ ከየት መጣ አልልም፣ ይሄው አንገቴ ላይ የለማዳ ውሻ ሰንሰለት መስሎ- ቱ! አንዲት የባንክ
ሰራተኛ ከአዲስ አበባ መቀሌ ተቀይራ ስትሄድ፣ “ምንም እቃ አላንዘፋዝፍም እዛው የሚያስፈልገኝን እገዛለሁ” ስትል፣ ቤቷ በውድ ዕቃዎች ተሞልቶ ስመለከት እንዴት?' አላልኩም ...
👍303😁2
ቱ! እኔ ደግሞ፣ “እንዳንተ የሚታገስ ወንድ አይቼ አላውቅም” ስትለኝ ካየችው ማወዳደሯን በምን አባቴ
ጠርጥሬ። ሰው ትንሽ እንኳን ምልክት ሳይታይበት ጣናን የሚያህል የፍቅር ሐይቅ ፍቅረኛው አፍንጫ
ስር ተደብቆ ይገድባል ? ኧረ ገረመኝ፤ ከምር ገረመኝ ! የሆነ ፀሐይ ወርዳ እዚህ አራት ኪሎ ላይ የተከሰከሰች ነገር መሰለኝ። ሙና የኔ ፍቅር ምንድነው ያደረግኳት .. እርሷኮ ነፍሴ ነበረች። አንድ ነፍስ
ለሁለት ወንድ ይካፈላል እንዴ። እሺ እኔ ያጎደልኩባት ነገር እንዲህ የበቀል ብትር የሚያሰነዝር ነበር ?
በቀል ይሁን ምናባቴ አውቃለሁ ? እንደው ምን እንደምለው ቸግሮኝ እንጂ ..

ሔዋን ቀስ ብላ መጥታ ጎኔ ተቀመጠች - ሔዋን የሙና ጓደኛ። እናም ትካሻዬ ላይ እጄን ጣል አድርጋ
እንዲህ አለች፣

አብርሽ በናትህ እንደሱ አትሁን” ዓይኗን አንከባለለችው። ያላት ውበት እሱ ብቻ ነው መቼም።

አንቺ ታውቂ ነበር ሙና ከእኔ ጋር ሆና ሌላ ወንድ ጋር ፍቅር እንደ ጀመረች ?”

በእውነት አላውቅም!እኔም ቪዲዮውን ሳየው ገርሞኛል”
ዓይኖቿ ተስለመለሙ። ሔዋን እጇ ትከሻዬ ላይ ነው። በጣም ተጠግታኛለች። እና ዝምታችን የሆነ ድባብ አለው። ሔዋን በጣም ተጠግታኛለች።
እንደውም አንዲት የቆመች ፀጉሯ በስሱ ጆሮዬን ስትነካኝ ተሰማኝ።
ምን ተፈጠረ ? ሔዋንን እያየኋት ወንድነቴ ነፍስ ሲዘራ ተሰማኝ። ማመን አልቻልኩም፤ ሱሪዬን
አውልቄ በዓይኔ ላየው ዳድቶኝ ነበር።ሔዋን ጎኔ ናት፤ እጄን አንስቼ ትከሻዋ ላይ አሳረፍኩት፤ ጠጋ
አለች እና እንዳቅፋት ተመቻቸችልኝ። እንደውም ራሷን ትከሻዬ ላይ ዘንበል አደረገችው። ወንድነቴ ዘራፍ ማለቱ እውን ሆነ።

ለሃኒባል ደውሉና ቆመ በሉልኝ !! አብሮኝ ተንከራትቷል። ቋሚ ይቆም ዘንድ አብሮኝ በችግሬ ለቆመ ቁም ነገረኛ ወዳጄ እመብርሃን በችግርህ ከጎንህ ትቁም በሉልኝ!ሙና ግን መንፈሷ የተኮላሸ ሴት ናት።
ልከስክስ !! መቶ ዓመት ለማይኖርባት ምድር ረክሶ ተልከስክሶ እና አስመስሎ መኖር ክብር መስሏት ቆይ ዘላለም ላይ እንገናኝ የለ!
፡፡፡፡፡፡፡፡።፡
የሔዋን መኝታ ቤት እንዴት ሰፊ ነው ? ሔዋን ደረቴ ላይ በእርካታ ተኝታ እንዲህ አለችኝ፣ “አንተ
የሚወራው ሁሉ ውሸት ነው ማለት ነው ...ውይ የሰው ወሬ"

"ምን ተወራ"

" እንትን አይችልም እየተባለ ነዋ የሚወራው”

“ማነው ያለው” አልኩ ታሪኬን ሐሰት ልል እየተንደረደርኩ።"

“የድሮ ሚስትህ ነቻ” ሙንዬ፣ ሙኒት፣ ሙንሻ የምትላት ጓደኛዋን “የድሮ ሚስትህ” ስትል አይቀፋትም ?

“ባክሽ እሷን ተያት” እቅፍ እቅፍቅፍ … እቅፍፍቅፍቅፍ !! ያልታቀፈበት ዘመናችንን ቀይ የሙና ገላ በጥቁር የሔዋን ገላ መቀያየሩ አልጋ ላይ የተዘረፈ ቅኔ ነገር ነው ... ይነጋል ይመሻል እንደማለት !

“አንተ አፈ ን ከ ኝ ሂሂሂ” ሔዋን የሙናን ፍቅረኛ በፍቅር አሸንፋ ራሷን የድል ማማ ላይ አስቀምጣ
ተፍነሽንሻለች። የሙና ባል እኔን አሸንፎ፣ሙናም እኔን አታልላ በብልጠት አልፋኝ እንደሄደች ሳይሰማት አልቀረም። እኔም ደስ አላለኝ አልከፋኝ፤ እንደው ደርበብ ባለ አብሮነት ዝምታን መረጥኩ። ለምን ደስ ይለኛል? ማፍቀር ተኮላሽቶ ወንድነት ስለቆመ? እንዲህ ዓይነቱን ደነዝ ወንድ የሚያመርተው፣ ደነዝ ክህደት ... ለሙና ሆነ!! መቼም ቢሆን አፉ አልላትም፤ ምክንያቱም አፈቅራታለሁ።


አለቀ
👍33👏3👎2
አትሮኖስ pinned «#ቀስ_ብሎ_ይቆማል ፡ ፡ #ስምንት (የመጨረሻ) ፡ ፡ #በአሌክስ_አብርሃም ...“ቆይ አብርሸ ምንድን ነው … ማለቴ…ተወው በቃ” ግራ ተጋባች። እናም እንዲህ አለችኝ፣ ችግር የለውም እንዳታስብ፣ ምንም ነገር እንዳታስብ !” ስትናገር ዓይኔን ማየት ፈርታ ነበር።እጆቿ እነዛ ቆንጆ ጣቶቿ በሆነ ፍርሃት ሲንቀጠቀጡ ይታዩኛል። ብርድ ልብሱን ከጎኔ ገልባ ሸርተት ብላ ገባች። ወዲያው ተመልሳ ተነሳችና የሌሊት…»
💚💛❤️አድዋ💚💛❤️
👍6🔥2
#አድዋ

አድዋ ነጭ ነዉ አድዋ ጥቁር
አድዋ ነፍስ ነዉ አድዋ ፍጡር
በአጥንት ተዋጅቶ በደም የሚኖር
ህሊና ማይሽረው የተኖረ ተዓምር
ማን አለ እንደኛ ጥቁር የጥቁር ዘር
አድዋ ስሜ ነው ለእኔነቴ ክብር
የአለም ጥቁር ዋጋ የህልውናው ሚስጢር
ትላንት ነኝ ዛሬ በሞቱት የምኖር፡፡

እንኳን ለ 126 ተኛው
#የአድዋ_ድል አደረሳችሁ።

💚 💛 ❤️
12👍3🔥2
#ዓድዋ
ዋ! ..... ያቺ ዓድዋ
ዋ! ...
ዓድዋ ሩቋ፣
የአለት ምሰሶ አድማስ ጥግዋቋ፣
ሰማይ ጠቀስ ጭጋግ ዳስዋቋ።
#ዓድዋ.....
ባንቺ ብቻ ሕልውና፣
በትዝታሽ ብፅዕና፣
በመስዋዕት ክንድሽ ዜና፣
አበው ታደሙ እንደገና።
ዋ!
ዓድዋ የዘር ዐፅመ ርስቷ፣
የደም ትቢያ መቀነቷ።
በሞት ከባርነት ሥርየት፣
በደም በነፃነት ስለት፣
አበው የተሰውብሽ ለት።
#ዓድዋ!
የኩሩ ትውልድ ቅርስዋ፣
የኢትዮጵያነት ምስክርዋ።
#ዓድዋ
የኩሩ ደም ባንቺ ጽዋ፣
ታድማ በመዘንበልዋ።
ዐፅምሽ በትንሳኤ ንፋስ፣
ደምሽ በነፃነት ሕዋስ።
ሲቀሰቀስ ትንሳኤዋ፣
ተግ ሲል ሲንር ትቢያዋ፣
ብር ትር ሲል ጥሪዋ፣
ድው እልም ሲል ጋሻዋ፣
ሲያስተጋባ ከበሮዋ፣
ሲያስገመግም ዳኘው መድፍዋ።
ያባ መቻል ያባ ዳኘው፣
ያባ ነፍሶ ያባ ቃኘው፣
ያባ በለው በለው ሲለው፣
በለው በለው በለው በለው።
ዋ! ...... #ዓድዋ .....
ያንቺን ፅዋ ያንቺን አይጣል፣
ማስቻል ያለው አባ መቻል።
በዳኘው ልብ በአባ መላው፣
በገበየሁ በአባ ጎራው፣
በአባ ነፍሶ በአባ ቃኘው፣
በለው ብሎ በለው በለው።
ዋ! ...... #ዓድዋ .....
ዓድዋ የትናንትናዋ፣
ይኸው ባንቺ ሕልውና፣
በትዝታሽ ብፅዕና፣
በመስዋዕት ክንድሽ ዝና፣
በነፃነት ቅርስሽ ዜና፣
አበው ተነሱ እንደገና።
....... ዋ! ........ ያቺ ዓድዋ፣
ዓድዋ ሩቅዋ ፣
የአለት ምሰሶ አድማስ ጥግዋ፣
ሰማይ ጠቀስ ጭጋግ ዳስዋ።
#ዓድዋ .......

🔘ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን🔘
👍13
‹‹ዓድዋ››

የሰው ልጅ ክቡር፣
ሰው መሆን ክቡር፣
ሰው ሞቷል ሰው ሊያድን፣
ሰውን ሲያከብር፣
በደግነት፣ በፍቅር፣ በክብር ተጠርቶ፣
በክብር ይሄዳል፣ ሰው ሊኖር ሰው ሞቶ።
የተሰጠኝ ሕይወት ዛሬ በነፃነት፣
ሰው ተከፍሎበታል ከደምና ከአጥንት፣
ስንት ወገን ወደቀ በነፃነት ምድር፣
ትናገር ዓድዋ፣ ትናገር ትመስክር፣
ትናገር ዓድዋ፣ ትናገር አገሬ፤
እንዴት እንደቆምኩኝ ከፊታችሁ ዛሬ።
በኩራት፣ በክብር፣ በደስታ፣ በፍቅር፣
በድል እኖራለሁ ይኸው በቀን በቀን፣
ደሞ መከራውን ያን ሁሉ ሰቀቀን።
ዓድዋ ዛሬ ናት ዓድዋ ትናንት፣
መቼ ተነሱና የወዳደቁት፣
ምስጋና ለእነሱ ለአድዋ ጀግኖች፣
ለዛሬ ነፃነት ላበቁኝ ወገኖች፣
የጥቁር ድል አምባ፣ ዓድዋ፣
አፍሪካ፣ እምዬ ኢትዮጵያ፣
ተናገሪ የድል ታሪክሽን አውሪ።

#እጅጋየሁ_ሺባባው (ጂጂ)
👍135
#አታውቃት_እንደሆን

ሰው እንደ ሰው ቢቆም፥በእናት ሐገር ምድሩ
ያለዋጋ አይደለም፥ወዲህ ነው ምሥጢሩ
አያት ቅድመ አያቱ ፥ ጠላትን ሲመቱ
እንደዝናብ ሲወርድ ፥ የጥይት መዓቱ
ሲንጣጣ ሲያሽካካ ፥ ጦር አውርዱ ኹላ
ያፈገፈገ የለም ፥ ከቶም ወደ ኋላ።
ከኋላ ምሽት አለች ፥ ከአንድ ወንዝ የተቀዳች
ከቀሚሷም ወርዶ ፥ የሚድኹ ልጆች
የእርሻም መሬት አለ ፥ በላብ ወዝ የራሰ
የሽምብራ ጥርጥር ፥ በወግ ያደረሰ
የቤተስኪያን ደውሉ ፥ የመስኪድ አዛኑ
ኢምንት እምነቱ ናት ፥ የሰው ማዕዘኑ።
አይሸሽም አይፈራም ፥ ያቅራራል ቀረርቶ
ሽለላ ያሰማል ፥ ዘራፍ ደረት ነፍቶ
ግዳይ እንደ ጣለ ፥ በሞት ነው የሚፈካ
ከጠላ ጠላ ነው ፥ ከማረም አይነካ
ጀግና ዕድሜ እየተጫነው ፥ ምን በመልኩ ቢጃጅ
ፈርቶ ሞት አያውቅም ፥ ጦር ቀምሶ ነው 'ሚባጅ።
ቆመህ ስትራመድ ፥ ዛሬ በነጻነት
ደፍረህ ስትናገር ፥ ቀና ብለህ ካንገት
ትርጉሙ እንዲገባህ ፥ ውሉን እንዳትስተው
ኢትዮጵያዊነትህን ፥ ሀ ብለህ መርምረው።
የማንነት ካስማዋ ፥ የአንድነት ማማዋ
አታውቃት እንደሆን ፥ ይህቺው ናት #ዓድዋ

🔘እሱባለው አበራ🔘
👍3
#አድዋ_ዛሬ_ናት_አድዋ_ትላንት


#በአሌክስ_አብርሃም

(አንቀፅ 17 ፡ እኛም መስኮታችንን አንከፍትም፣ እናንተም ሚስቶቻችንን አትዩ ፡)

ጣሊያን ኢትዮጵያን ወርራ አምስት ዓመት ፍዳዋን በልታ፣ ፍዳችንን ስታሰበላን አያቴ እሳት የላሰ
የውስጥና የውጭ አርበኛ ነበር። በጦር ሜዳ ብትሉ አንድ ባታሊዮን ጦር ጭጭ ምጭጭ ያደረገ
ጀግና ሲሉት፣ “ኤዲያ ምን አላት እቺ” ይላል !! በከተማ ብትሉ" ጠላት መኝታ ቤት ሳይቀር የተቀመጠ ሚስጥር ፈልፍሎ ሲያወጣ አጀብ ያስብል ነበር። ታዲያ በአያቴና በቆራጥ አርበኞች ትግል ፋሺስት ኢጣሊያንን ከሀገር ከተባረረ በኋላ፣ ለአገር በሠራው ታላቅ ጀብዱ፣ በድል አጥቢያ ጃንሆይ ራሳቸው አስጠርተው አሁን የጣልያን ኤምባሲ የሚባለው የተገነባበትን ቦታ በሙሉ ከታላቅ ክብርና ምስጋና
ጋር በሽልማት ለኢያቴ ሰጡት !

አያቴ እዚሁ በሽልማት የተሰጠው ቦታ ላይ ትንሽ ጎጆ ቀልሶና፣ የተረፈው ሜዳ ላይ የቆሎ ዘርቶ
ሲኖር፣ አንድ ቀን የጃንሆይ መልዕክተኞች ሲገሰግሱ ቤቱ ድረስ መጡና፣

“እዚህ በቆሎ የዘራህበት ቦታ ላይ የንባሲዮን ሊሰራሰት ነውና መድረሻህን ፈልግ ብለውሃል ጃንሆይ አሉት።

“ኧረ ውሰዱት ደሞ ለሞላ ቦታ አላቸው። ትንሽ ቆይቶ፣ “ይሄ ግን 'የንምባሲዮን' ያላችሁት ነገር መንግስት ነው ?” ሲል ጠየቀ።

“አይደለም !"

“አሃ ተማሪ ቤት መሆን አለበት :"

“አይደለም!”

ታዲያ ምንደን ነው ቤተስክያን ይሆን እንዴ ?" ሲል ግር ብሎት ጠየቀ።

"ኤማቢሲዎን ማለትንጉሥ የፈቀዱላቸው የውጭ አገር መኳንት እና መሳፍንት አገራቸውን
መስለው የሚቀመጡበት እና አንዳንድ የመንግሥት ሥራዎችን የሚከውኑበት ማረፊያ ነው" አሉት
ሳኔ ዕክተኞቹ አንዱ። ከመልክተኞቹ አንዱ።

"በቃ ?" ሲል ጠየቀ አያቴ በግርምት።

"በቃ!"

"እኮ ፈረንጆች ይሄን ሁሉ ቦታ አጥረው ቁጭ ሊሉ ነው” አለ እንደገና በታላቅ ግርምት።

"አዎ ! ይሄ የምባሲዮን ... የወከላቸው አገር የማይደፈር ግዛት ነው”

እንዲያ ድንበራችን ላይ ያባረርነውን ጠላት መናገሻችን ላይ አርደንለት ጋርደንለት ልናስቀምጠው ነው በለኛ አለ አያቴ በቁጭት።

መልዕከተኞቹ አያቴ ላይ ሳቁበት። ስለኤምባሲ ያለው እውቀት አነስተኛ መሆኑን በመገንዘባቸው
ድፍን ሁለት ሰዓት ስለኤምባሲ ተግባርና ለአጎራችን ስላለው ጠቀሜታ በዝርዝር አወሩት።

ተግባብተው ሊለያዩ ሲሉ ግን ነገር ተበላሽ።ጉድፈላ። አገር ተሸበረ።ድንገት ነው ነገሩ የተመሰቃቀለው

ከሆነስ ሆነና የማን አገር ኤምባሲዮን ነው ?" ሲል ጠየቀ አያቴ፣

“ጥልያን” ብለው መለሱለት።

"ጥልያን ጥሊያን ... እኮ ጥሊያን ይሄ ፋሽስት የነበረው" አለ አያቴ ማመን አቅቶት።

"እንዴታ አሁን በሰላም መጥተዋል”

አያቴ ሰይጣኑ ተነሳ። ተንደርድሮ ምንሽሩን መዥረጥ አደረገና ለግማሽ ሰዓት ያህል ፎክሮ ሲያበቃ፣

"ባንዳ ሁላ…” ብሎ የጃንሆይን መልዕክተኞች ማሳደድ ጀመረ !

ጥሎብን መከተል እንወዳለን። መንገድ ላይ ድንገት አያቴን ያዩ ሁሉ፡ ገና የአርበኝነት ስሜቱ
ያልበረደላቸው፣ እንዲሁም አርበኝነት ያመለጣቸው፣ እንደገና እድሉን አገኘን በማለት ምንሽራቸውን አፈፍ እያደረጉ፣ “ያዘው…" እያሉ ላይጠቅማቸው አያቴን ተቀላቅለው የንጉሱን መልእክተኞች ማሳደድ ጀመሩ። መቼስ አዲሳባ እንደዛን ቀን ተፎክሮባትም፣ ተሸልሎባትም አያውቅም ሲሉ ሁኔታውን የታዘቡ፡፡

አያቴ ቁጣው መለስ ሲል ዞሮ ቢመሰከት ድፍን የአዲስ አበባ ወንድ ተከትሎታል።

“ምን ሆናችሁ” ቢላቸው አያቴ፣ “አይ ሩጫው ወደ ቤተ መንግሥት መሆኑን ስንሰማ ነው
የተከተልኛችሁ” አሉ !!

አያቴ የተከታዩን ብዛት አየና በዛው ሸፈተ ! ስሙ የገነነ ሽፍታም ሆነ ! ስሙ ከተጠራ እንኳን ኢትዮጵያ
ምድር ያሉት ሮም የተቀጡትም ጥልያኖች ወባ እንደያዘው እየተንዘፈዘፉ ንሰሃ ይገባሉ ! ጭራሽ የኤምባሲው ግንባታ ሲጀመር በወርም በሳምንትም በል ሲለው በየሦስት ቀኑ ብቅ እያለ ይሄን ጣልያን ሁሉ ይፈጀው ጀመረ !!

ጃንሆይ በበኩላቸው አያቴን በዲፕሎማሲ ማሳመን መርጠው መልዕክት ላኩበት። በድፍረት ከነጎፈረ ጸገሩና ከነምንሽሩ ፊታቸው ቀርቦ፤ "ጃንሆይ ትላንት ይሄን ፋሽስት፣ እንኳን አሳረርከው' ብዬ የሸለሙኝን ቦታ ዛሬ ከኔ ነጥቀው ላባረርኩት ሰላቶ በመስጠትዎ ተቀይሜዎታለሁ !! እማምላክን ተቀይሜዎታለሁ። እንዴት እንዴት ነው ነገሩ ... እዚህች አገር አባራሪው ከተባራሪው ተደባለቀ እኮ
ዳር ላይ ያባረርነው ከመሐል እያባረረን ተቸገር?" አለ።

ጃንሆይ በጥሞና ሲያደምጡ ቆዩና፣ “ቅሬታህን ሰምተናል። ካንተ የሚበልጥብን የለም። ያው አንተ ዳር ላይ ልክ ያስገባሃቸው ናቸው ዛሬ ወዳጅነታችንን ፈልገው በእንብርክክ ደጅ የጠኑን
እንደምታውቀው ጀግና በጠብ የመጡበትን አንጂ በፍቅር የመጣን አይነኩም አሉና የአያቴን ቁጣ አበረዷት።

“በል አሁን በቃህ ለማን ብለህ ነው መሬትህን ጥለህ የምትሄደው፡፡ እነሱ እያዩህ ይሸማቀቁ እንጂ ብለው እዛው ኤምባሲው ጎን ለአያቴ ሰፊ ቦታ ሰጡት።

እርቅ ወረደ! ንጉሡ ብልህ ነበሩ። አንዳንዴ አያቴን ይጠሩትና፣ ጎረቤቶችህ ሰላም ናቸው ? ብለው
ይጠይቁታል። አያቴን ሰላይ አደረጉት እንግዲህ የአያቴ ጎጆ እና የጣሊያን ኤምባሲ በግንብ አጥር ብቻ ነበር የሚለያዩት። አያቴ ጣልያኖቹን ባያቸው ቁጥር ደሙ እየፈላ፣ "ወይ ነዶ የማንም ፋሽስት ጋር እንዲህ ትከሻ ለትካሻ እየተጋፋሁ ልኖር” እያለ በብስጭት ሲግል ሚስቱ ወይዘሮ በልጅጌ መኮንን (የፊታውራሪ መኮንን እጅጉ የመጀመሪያ
ልጅ እያባበለች ወደ መኝታ ቤታቸው ትወስደውና ከብስጭቱ አብርዳ በሌላ ጉዳይ ትለኩሰዋለች ! አቤት ማባበል ስታውቅበት …. ገና ስትታይ ነገር ታበርዳለች ... እሳት ፈገግታዋ እሳት ያጠፋል ... ይች ውብና አስተዋይ ሴት ሲበሳጭ ስታባብለው፣ ሲበሳጭ ስታባብለው .… አምስት ሴትና አንድ ወንድ ልጅ ወለዱ። ይሄ ብቸኛ ወንድ ልጅ የእኔ አባት ነበር።

አያቴ ምንም እንኳን የልጆቹን አእምሮ በምክር አርሶና አለስልሶ የጣሊያንን ጥላቻ ቢዘራበትም
አልፀደቀም። በተለይ ሴት ልጆቹ ያማረ መኪና ይዘው የሚገቡና የሚወጡ የጣልያን ጎረምሶች ላይ
ልባቸው አልጨክን እያለ፣ ዓይናቸውም እየተንከራተተ አስቸገረው። ጭራሽ ይለይልህ
ብለው ከአባቴ በስተቀር ሁሉም ሶላቶ' አግብተው ቁጭ አሉ። በዚሁ ብስጭት ሙሉ ቦታውን ለአባቴ ብቻ አውርሶና ጥልያን ያገቡ ልጆቹን ሁሉ ክዶ ሚስኪን አያቴ በደም ግፊት ሞተ !! አባቴም፡ 'ሙሉ' የምትባል ውብ
ሴት አግብቶ እዚሁ ነገረኛ የወርስ ቦታ ላይ ቤት ሰርቶ መኖር ጀመረ (ሙሉ እናቴ ናት…)።

እናቴ ሙሉ መቼስ ወላ በቁንጅና፣ወላ ሰባሕሪ ቢባል ይሄ ቀረሽ የማትባል ውብ ናት። ስትገባ ስትመጣ ተመልካቹ በዛ፣ የሚመኛት እልፍ ነበር። አባቴ ታዲያ እናቴ ስትደነቅና ስትሞገስ ደስ ቢለውም፣ ከተመልካቹ ሁሉ ደሙን የሚያፈላው የጣልያኖቹ አስተያየት ነበረ። እንግዲህ ጣልያኖቹ እናቴ ስታልፍ ፊታቸው እንደ ቲማቲም ቀልቶ አፋቸውንም፣ ዓይናቸውንም በልጥጠው በአጥራቸው ላይ እየተንጠላጠሉ በአጉል ምኞት ሲመለከቷት አባቴ ይሰሳጫል፤ በላቸው በላቸው ይለዋል። (ደግሞ ለማለት፣ አያቴ እንደሆነ ምንሽሩን አውርሶታል- መታገስ ደግ ነው ብሎ እንጂ…)
👍15🥰1
ምድረ ሰላቶ ከዘበኛ እስከ አምባሳደር ማፍጠጣቸው ሳያንስ፣ “ለደህንነት” በሚል ሰበብ ፊታቸውን ወደ እኛ ግቢ ያዞሩ አራት ካሜራዎች ተከሉ። እናቴ ግቢ ውስጥ በተንቀሳቀሰች ቁጥር አራቱም ካሜራዎች ወደሄደችበት ተከትለዋት ይዞራሉ (የምታጠባቸው መንታ ልጆቿ ነበር የሚመስሉት)። ሌላ ሰው ሲንቀሳቀስ ካሜራዎቹ ግኡዝ ናቸው። ካሜራዎቹ የተተከሉት ለደህንነት ይሁን ላጉል ምኞት
አባቴ ግራ ገባው።

ጭራሽ ጥልያኖች ባሳተሙት አንድ ዓመታዊ መጽሔታቸው ላይ እናቴ አጎንብሳ አሮጌ የመኪና ጎማ
ላይ በተቀመጠ ጥሰት ልብስ ስታጥብ ከኋላዋ (ያውም አጭር የውስጥ ልብስ ብቻ ለብሳ) የሚያሳይ ባለቀለም ፎቶ ተካትቶ ነበር። ከእናቴ ፎቶ ጎን አንዲት ጥላ ቢስ፣ ሽርጥ ያሸረጠች ጣልያናዊት ኮረዳ ዘመናዊ የልብስ ማጠቢያ ማሽን ደገፍ ብላ የሚያሳይ ፎቶ አለ።

ከፎቶዎቹ ሥር፣ “ኢትዮጵያ ከጣልያን ስድስት ዘመናዊ የልብስ ማጠቢያ ማሽኖች ለእርዳታ አገኘች ይህም የኢትዮጵያዊያንን ሴቶች ድካም በመቀነስ ጊዜያቸውን ለሌላ ጉዳይ እንዲያውሉት ይረዳሉ የሚል ጽሁፍ ሰፍሯል። ሌላው ጉዳይ' ምንድን ነው ሲል አባቴ አሰበ።
እንዴት የሚስቴኝ ፎቶ ካለ እሷም ካለእኔም ፍቃድ መጽሔት ላይ ያትማሉ፣ ሲል ተብከነከነ፡
እንደውም አምባሳደሩን ራሱን ማብራሪያ እንዲሰጠው ሊጠይቀው ወሰነ። ሰውን ካለፍቃዱ፣ ያውም በገዛ ግቢው ውስጥ፣ እንዴት ፎቶ ያነሳሉ … ያውም በአጭር የውስጥ ልብስ ብቻ ይሄ ንቀት ነው

አባቴ በቀጥታ ወደ ኤምባሲው ዋና በር ሄደና እንደ ግለሰብ መኖሪያ ቤት አስፈሪውን የብረት በር አንኳኳ፣

ጓጓጓጓጓ

ዘበኛው አጨንቁሮ አባቴን ከተመለከተ በኋላ በሩን ከፍቶ ባለማመን እያየው፣

“ምን ፈለግክ ?” አለው እርዳታ የፈለገ ኢትዮጵያዊ ይሆናል ብሎ፣

“ጌታህን ጥራው ! ባልቻ በርህ ላይ ይፈልግሃል አለው" አለ አባቴ ቆፍጠን ብሎ። ዘበኛው ግራ ተጋባና፣

“ማንን ነው የጥበቃ አልቃውን ነው ?” አለ።

“እሱ ምን ያደርግልኛል ?
አምባሳደሩን ነው ያልኩሆ

"እ ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ … በል ሂድ ወደዛ ደፋር ብሎት እርፍ አባቴ ባልቻን !

መንደሩ የተከበረውን ኣባቴን እንደ ምጽዋት ፈላጊ የሶላቶዎቹ ዘበኞ፣ ሂድ ወደዛ አለው ! በዛችው
ቅፅበት ከአባቴ የተሰነዘረ ብርቱ ጥፊ ዘበኛውን አባቴ እግር ሥር ኩርምት አደረገው። የጥፊው ድምጽ ሮም ድረስ ስለተሰማ፣ የውቅቱ የጣሊያን መንግሥት፣ ኢትዮጵያ ዓለማቀፉን የኤምባሲዮን ውል እና አሰራር በመተላለፍ የተከበረ ዜጋዬን በጥፊ በመደርገም በአድዋ ካደረሰችብኝ ውርደት የበለጠ
ውርደት አድርሳብናለች ሲል ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አቤት አለ።
ጃንሆይም በዚሁ ጕዳይ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡ ተጠይቀው፣ “በእርግጥ አፍሪቃ ኤሮፓዊያን ቅኝ ግዛት እየታመሰችበት ባለችበት በዚህ ወቅት፣ ብዛሃን የአፍሪቃ ልጆች በቆዳቸው ቀለም ምክንያት በግፍ እየተገደሉ እና እየተገፉ ባሉበት ወቅት፣ በአንዲት ኤሮፓዊት አገር ኤምባሲ የጥበቃ ሰራተኛ ላይ፣ ያውም በራሱ ስህተት፣ በተሰነዘረ ጥፊ ዓለም ይህን ያህል መንጫጫቱ ገርሞናል። ይህ ጥፊ የኢትዮጵያ መንግሥትን የማይወክል፣ በዕለት ግጭት የተከሰተ ድንገተኛ ጥረቀማ በመሆኑ ግለሰቦቹ
በቀላል ሽምግልና ችግሩን እንዲፈቱት እናደርጋለን። አገራችንም ከጥፊው ባሻገር ለአፍሪቃ ብሎም ለዓለም ያበረከተችው ቀጎ ተግባር በዚህ ጥፊ ምክንያት ሊጠለሽ አይገባም” በማለት ዓለምን ያስደነቀ፣ አገሬውንም ያኮራ ንግግር አደረጉ።

በዚህ ንትርክ መሃል የእናቴ ፎቶ ጉዳይ ተድበሰሰሰ።

በጣልያኖች ተንኮል እልህ የተጋባው አባቴ፣ “ልጆቼ ስለበረከቱ ፎቅ ቤት እሰራለሁ…” አለና ማንንም ሳያስፈቅድ ባለ ሁለት ፎቅ ቪላ ወደ ኤምባሲው አጥር እስጠግቶ መሥራት ጀመረ።

ይሁንና ጣልያኖች ለደህንነታችን ያሰገናል በማለት ክስ አቀረቡ።

ኤምባሲ ጎን ፎቅ መሥራት ክልክል ነው ተብሎ አባቴ ታገደ

አገሬ ላይ እስከ ጨረቃስ ፎቅ ብሥራ ምን አገባችሁ ?” በማለት ጠየቀ።

“ለወዳጃችን የጣልያን መግሥት ስጋት ስለሚፈጥር፣ ለደህንነታቸውም ስለሚያሰጋ አይፈቀድልህም አቶ ሳልቻ”

አሄሄ እነሱን ለመግደል ማን ፎቅ ይሰራል … ውቤ በረሃ ሲያውደለድሉ አይደለም የሚውሉት…”

ሥርዓት ጌታው፣ እንግዶቻችንን ማክበር የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ግዴታ ነው”

ጉዳዩ በጣም ተጋነነና በአባትና በጣልያኑ አምባሳደር መካከል የሁለትዮሽ ድርድር ሲካሄድ የተሻለ
ነው በማለት በጃንሆይ ልዩ አማካሪዎች አስተባባሪነት በጣልያን መንግሥትና በአባቴ ባልቻ መካከል ታሪካዊ ድርድር ተካሄደ።

ይህ ድርድር በታሪክ፣ አንቀጽ 17 - እኛም መስኮታችንን አንከፍትም እናንተም ሚስቶቻችንን አትዩ”
በመባል ይታወቃል

የውሉ ዋና ዋና ነጥቦች!

አንቀፅ 1. አቶ ባልቻ ደመቀ ኤምባሲያችን ጎን የሚሰሩት ፎቅ መስኮቱ ወደ ጣልያን ኤምባሲ ላይ ላይዞር ከዞረም ላይከፈት።

አንቀፅ 2. ጣልያኖች ወደ ኤምባሲው ሲገቡና ሲወጡ አሁን ያሉትንም ሆነ ወደፊት የሚወለዱትን የአቶ ባልቻን ሴት ልጆች በቃልም ሆነ በድርጊት ላይተናኮሱ፧ በመኪናም ሆነ በእግር በር ላይ ላይንጎማለሉ
ሆን ብለው ስሜት ቀስቃሽ እና አማላይ ድርጊት ላይፈፅሙ።

.
.
.
.
.
.
አንቀጽ 17. ወደ አቶ ባልቻ ቤት የዞሩት የኤምባሲው የቪዲዮም ይሁኑ የፎቶ ካሜራዎች ሙሉ በሙሉ እንዲነሱ።

የዚህ ውል 17 ኛው አንቀጽ የጣልያኑ ትርጉም ግን እንዲህ ይል ነበረ፣

የኤምባሲያችን የቪዲዮም ይሁኑ የፎቶ ካሜራዎች፣ የሙሉን እንቅስቃሴ ሙሉ ለሙሉ ፎቶ ሊያነሳ ፈቃድ አላቸው ይላል።

ታሪክ ራሱን ይደግማል !!

እናቴ ሙሉ ታዲያ ከንፈሯን ሸምም አድርጋ የተንኮል ፈገግታ ፈገግ አለች። ማንም አላያት ከሰይጣን
እና ከእኔ በስተቀር። ትንሽ ወንድሜ አባቴን አለመምሰሉ እንደውም ፈረንጅ መምሰሉ እስቋት ይሆን.!

አለቀ
👍14🤔1
#አድዋ_በአፍ_አይገባም

አድዋ የደም ግብር ነው፤ አበው የለኮሱት ቀንዲል
አድዋ የአፍሪካ ዱካ ነው፤ አበሽ የከተበው ፊደል
ላጥፋህ ቢሉት መች ይጠፋል፤ ጠላት በልቶ ያፈራ ተክል
ለዛሬም ታሪክ አባት ነው፤ “ነገም ሌላ ቀን ነው” ለሚል
አድዋ ሰው ዛብ፣ የደም ድልድይ
አንድም ፍልሚያ፣ አንድም ራእይ
ልብ ላለው ልብ ያነዳል
ለምር ቀን ስንቅ ይሆናል!!
ነጻነት አይለመንም
ያው ጥንትም ተጽፏል በደም
አገር ድንበሯ ሲነደል፣
ያው ዛሬም ተማግሯል በፍም
የአጋም አጥር ተደግፎ
ጎረምሳ ኮረዳም ቢስም
በወርቅ አልጋ በእርግብ ላባ
ተኝቶ ማደር ቢቻልም
አገር ከፍቷት ሰላም የለም
አድዋ ሞተው ሲኖሩ እንጂ ተተርኮ በአፍ አይገባም!
ዱሮም ዛሬም በአፍ አይገባም!


🔘በነቢይ መኮንን🔘
👍4
“የምኒልክ ፈረስ በክንፎቹ ሔደ”
ምኒልክ ተወልዶ ባያነሣ ጋሻ
ግብሩ እንቁላል ነበር ይኸን ጊዜ አበሻ፡፡
በሠራው ወጨፎ ባመጣው እርሳስ
ተፈጠመ ጣልያን አበሻ እንዳይደርስ፡፡
ምኒልክ ተጉዞ የምትጠይቁኝ
ፊትም አላለፈ ኋላም አይገኝ፡፡
መድፋን መትረየሱን ባድዋ መሬት ዘርቶ
እንክርዳዱን ነቅሎ ስንዴውን ለይቶ
የዘራውን እህል አጭዶና ወቅቶ
ላንቶኔሊ አሳየው ፍሬውን አምርቶ፡፡
እንዳቀና ብሎ ለምኖ መሬት
ንግድ ሊያሰፋበት ሊዘራ አትክልት
እየመጣ ሊሰጥ ግብሩን ለመንግሥት
ለጓዙ ማረፊያ አገር ቢሰጡት
ተጠማኝ ሰንብቶ ሆኖ ባለርስት
ወሰን እየገፋ ጥቂት በጥቂት
እውነት እርስት ሆነው ተቀበረበት፡፡
ባሕር ዘሎ መምጣት ለማንም አትበጅ
እንደ ተልባ ስፍር ትከዳለች እንጂ
አትረጋምና ያለተወላጅ፡፡
የዳኛው አሽከሮች እየተባባሉ
ብልት መቆራረጥ አንድነት ያውቃሉ
#ዓድዋ ከከተማው ሥጋ ቆርጠው ጣሉ፡፡
የእስክንድር ፈረስ መቼ ተወለደ
የምኒልክ ፈረስ በክንፎቹ ሔደ፡፡
ደንገላሳ ሲዘል እየተንጓደደ
የሮማውን ኩራት በእግታ አሰገደ፡፡
አገርህን ምኒልክ እንዳሁን ፈትሻት
እጁን ቀምሼ አላውቅም እያለ ሲያማህ
ቀመሰና እጅህን መጥቶ ጠላትህ
ሮም ላይ ተሰማ ለጋስ መሆንህ፡፡
አባተ በመድፋ አምሳውን ሲገድል
ባልቻ በመትረየስ ነጥሎ ሲጥል
የጐጃሙ ንጉሥ ግፋ በለው ሲል
እቴጌ ጣይቱ እቴጌ ብርሃን
ዳዊቷን ዘርግታ ስምዓኒ ስትል
ተማራኪው ባዙቅ ውሃ ውሃ ሲል
ዳኛው ስጠው አለ ሠላሳ በርሜል፡፡
እንደ በላዔ ሰብአ እንደመቤታችን
ሲቻለው ይምራል የኛማ ጌታችን፡፡

🔘ተክለ ጻድቅ መኩሪያ🔘
👍8👏1
‹‹ጣልያን ገጠመ ከዳኘው ሙግት
አግቦ አስመሰለው በሠራው ጥይት
አሁን ማን አለ በዚህ ዓለም
ጣልያን አስደንጋጭ ቀን ሲጨልም
ግብሩ ሰፊ ነው ጠጁ ባሕር
የዳኛው ጌታ ያበሻ ባሕር፡፡
ሸዋ ነው ሲሉት ዓድዋ የታየው
ሺናሻ መላሽ ወንዱ አባ ዳኛው
አይኮረትም እጁ የዘናው
ወንዱ ምኒልክ ዝንታለም ይቅናው፡፡
ወዳጁም ሣቀ ጠላቱም ከሳ
ተንቀሳቀሰ ዳኛው ተነሣ
አራቱ አኅጉር ለሱ እጅ ነሳ
ፈረሱ ዳኘው ሚስቱ ጣይቱ
ምጥዋ ቀዳች ያቺ ወጥ ቤቱ፡፡
👍10
#ትኩሳት


#ክፍል_ስምንት


#በስብሐት_ገብረ_እግዚአብሔር

ሲልቪ
ውስጥ ውስጡን


በነጋታው ጧት የመኝታዬ በር በኃይል ሲንኳኳ ነቃሁ፡፡ ማነህ
ሳልል በሩን ከፈትኩ። ሲልቪ እየሳቀች ዘላ ተጠመጠመችብኝ፡፡
ተንገዳግደን አልጋዬ ላይ ወደቅን። የፀጉሯ ሽታ ደስ አለኝ
«ዛሬ ምን ሆነሻል?» አልኳት
«ፈተናዬን በማእረግ አለፍኩ። ተነስ እንሂድ»
«የት? »
«ፓሪስ። ቀጥሎ ጄኖቫ፣ ከዚያ ሮማ፣ ናፖሊ፣ ፊሬንዜ፣
ከዚያ ኒስ፣ ማርሰይ፣ ኤክስ፡፡ ፕላኑን በሙሉ አውጥቻለሁ፡፡ «ጎበዝ አደለሁም?»
«ጎበዝ ነሽ፡፡ መቼ ነው «ምንሄደው?»
«አሁኑኑ፡፡ ተነስ ተጣጠብ» አለችኝ፣ ሰሰፊ ኣፏ እየሳቀች
«ለባለሆቴሉ 'ምከፍለው ገንዘብ አልያዝኩማ»
«እኔ ይዣለሁ»
«በምንድነው የምንሄደው?»
«በባቡር። ባቡራችን ልክ ከዘጠና ሁለት ደቂቃ በኋላ ከማርሰይ
ይነሳል፡፡ ቶሎ በል»
እንደዚህ አጣድፋ፣ ማንንም ለመሰናበት ሳልችል ፓሪስ
ወሰደችኝ። ከሁሉ ቅር ያሰኘኝ አማንዳ ዱቤን ሳልሰናበት መሄዴ
ነበር በሚቀጥለው አስር ሳምንት
ውስጥ ስለባህራም በብዙም
አላሰብኩም፡፡ ስለ ምንም ነገር በብዙ አላሰብኩም፡፡ ሀሳቤን ሲልቪ ሞልታው ነበር

ባቡሩ ሞልቶ ቆይቶን አንድ ላይ ቦታ ለማግኘት ባለመቻላችን
ፊት ለፊቴ ተቀመጠች። ሁለታችንም መፅሀፍ ማንበብ ጀመርን።ትንሽ አነብና ሰርቄ አያታለሁ፡፡ ረዥም ፀጉሯ ውብ ነጭ ፈቷን እንደ ጥቁር ሀር ከቦታል። በጣም ቆንጆ ናት፣ የደስ ደስ አላት አንዳንድ ጊዜ ሳያት ትይዘኛለች። ትጠቅሰኝና ሳቅ ትላለች፡፡ መልሼ እጠቅሳታለሁ፡፡ ንባባችንን እንቀጥላለን። አልፎ አልፎ አንድ ያልገባኝን ቃል እጠይቃታለሁ:: ፈረንሳዮቹ
ብርቱካን ይበላሉ፣ ያወራሉ፣ ፖም ይበላሉ፣ ጋዜጣ ያነባሉ፣ ሳንድዊች ይበሳሉ፣ ወይን
ይጠጣሉ፣ ባቡሩን ያዝረከርኩታል፣ ያቆሽሹታል፣ ዝነኛውን «የፈረንሳይ ባቡር ግማት» ይሰጡታል

አቪኞን ስንደርስ አንዲት ኣሮጊት ከአጠገቤ ተነሳችና፣ ገና
ከመነሳቷ ቦታዋ ላይ እንድ ሰውዬ ተቀመጠ። ከኣቪኞን እንደወጣን
የሲልቪ አይኖች ደጋግመው እዚህ ሰውዬ ላይ ያርፉ ጀመር።
ሰውዬውን አየሁት። ፀጉሩ ላይ ነጭ ዘርቶበታል፣ ምናልባት ያርባ
አምስት አመት ሰው ይሆናል። አይኖቹ ንፁህ ሰማያዊ ሆነው፣
ቀጠን ያለ ፊቱ በጣም ቆንጆ ነው:: ሳየው ጠላሁት። ንባቤን ቀጠልኩ፣ ግን የማነበው ሊገባኝ አልቻለም፡፡ ስርቄ ሲልቪን አየኋት።
ሰውዬውን በሰማያዊ እይኖቿ ብርህን ታየዋለች። እሷ እሱን ስታይ፣እኔ እሷን ሳይ፣ ንዴቱ ውስጤ ሲጠራቀም፣ ብዙ ጊዜ ሄድን ሳያት ያዘችኝ። አይኖቿ ተርገበገቡ፣ ወደ ታች አየች፣ ጉንጮቿ ደም ለበሱ፡፡ ማማሯ የንዴቴን ጥቁር ደመና የፍትወት ብልጭታ ሲሰነጣጥቀው ተሰማኝ። «ድንገት ሳብ ኣድርጌ ቀሚሷን ገልቤ ጭኖቿን ፈልቅቄ..

በመስኮቱ ወደ ውጭ ማየት ጀመርኩ፡፡ ለጥ ያለ ሜዳ መሬት
ረዥም ቀጭን የቤተ ክርስቲያን ደወል ቤት ሰማዩን እንደ መርፌ
ወግቶታል፤ አንድ ቀጭን መንገድ ከሹሉ ደወል ቤት ስር ወጥቶ
እየተጠማዘዘ ሄዶ አድማሱ ውስጥ ገብቷል፣ ሰማይና ምድር
የተሰፉበት ክር ይመስላል፡፡ መንደሩ እንደ ልጅነት ቀስ እያለ ወደ ኋላ እየተንሸራተተ ጠፋ
ዘወር ብዬ ሲልቪን አየኋት። ራሷን ወደ መፅሀፉ ደፍታለች፣
ፈቷ ደም እንደለበሰ ነው:: መፅሀፌን ማንበብ ጀመርኩ። አሁንም ቃላቱ አይኔን ዘልቆ እንጉሴ ውስጥ መግባት አቅቶት፣ አይኔ ብቻውን ያነባል። ሲልቪን አየኋት። አየችኝና ፈገግ አለች:: ሰማያዊ አይኖቿ ሳቂታ ናቸው፡ በጣም ቆንጆ ፈገግታ ኣሳየችው። እናቷን!

ንባቤን ቀጠልኩ። ከዚያ በኋላ እንደገና ደጋግማ ስታየው
አየኋት። አንድ ሶስት ጊዜ ያህል፣ ስታየው እንዳየኋት አይታ በጣም
አፈረች፥ አይኖቿ ተርገበገቡ፣ ጉንጮቿ ቀሉ፤ ንዴቴና ምኞቴ
ውስጤ እየታገለ አስጨነቁኝ
ሶስት ሰእት ያህል አለፈ

ከሊዮን በኋላ አንድ ሁለት ትንንሽ ከተማ እንዳለፍን ሰውየው
እግሮቹን የሚዘረጋ አስመስሎ የሲልቪን እግር ነካ፡፡ ቀና ብላ በውብ አይኖቿ በፈገግታ አየችው፡፡ በሰፊ እፏም ሳቅ አለችለት፡፡ ሰውዬው
በእግሩ እግሯን ማሻሸት ጀመረ። ቀላች። ውስጤ ስጋዊ ፍትወትና
ንዴት ታገለ፣ ንዴቱ አሸነፈ። እግሬን የምዘረጋ አስመስዬ የሰውዬውን ቅልጥም በኃይል መታሁትና፣ ዘወር ብዬ እያፈጠጥኩ

Pardon, monsieur» አልኩት (ይቅርታ መስዬ»)

ve vous en pries አለኝ («ኧረ ግድ የለም )

እግሩን ሰበሰበ። ፊቱ በንዴት ይሁን በእፍረት ደም ለብሷል።
ሲልቪን አየኋት። መፅሀፏን ታያለች፣ ፈገግታ ብጤ አፏ ዙሪያ
ይርበተበታል። ሰውየው የሲጋራ ፓኮ ከኪሱ አውጥቶ ወደ ሲልቪ
ዘረጋ፣ እየሳቀች ተቅበለችው:: አቀጣጠለላት ወደ ፓሪስ ነው : ሚሄዱት?» አለችው
«አዎን ማድሟዜል። እርስዎስ?» አላት ወሬ ጀመሩ። ብሽቅ አልኩ። ተነስቼ ትቻቸው ወጣሁ
መተላለፊያው ዘንድ አልፎ አልፎ የቆሙትን ፈረንሳዮች
እየገጨሁ Pardon! እያልኩ፣ አንድ አስር ሰረገላዎች እቋርጬ
ሂጂ ባቡሩ መጨረሻ ደረስኩ
ስመለስ ግማሽ መንገድ ላይ ቆምኩ። እቺ ንፍጣም!

ልታሰቃናኝ ፈልጋ አይደለም? እንደማልቀና ማወቅ አለባት። ግማሽ ሰአት እስኪያልፍ ወደሷ አልመለስም፡፡ ምን ያህል ግድ እንደሌለኝ ይግባት . .»

ግማሽ ሰአት እንዴት ረዥም ነው! ሰአቴን አስር ጊዜ አየኋት::
እሷ ታድያ አትንቀሳቀስም። አምስት ደቂቃ እንኳ ገና አላለፈም። ወደ ጆሮዬ አስጠጋኋት። ተኝታለች። የለም የለም፡ የባቡሩ ጩኸት
ድምፅዋን አላሰማ ስላለኝ ነው። . . . እኔና ሰአቷ ስንተያይ ሩብ ሰአት አለፈ። ከዚያ በኋላ ግን መቆየት አልቻልኩም፡፡ ሰዎቹን
እየገጨሁ «Partdom!» እያልኩ ወደነዚያ ውሾች መመለስ እንደ
ጀመርኩ፣ በመስኮቶቹ በኩል ቤቶች ብቅ እያሱ ወደኋላ ሽው ብለው ሲያልፉ ይታዩኝ ጀመር። አንድ ትንሽ ከተማ ደርሰናል፡፡ ባቡሩ በቆመልኝ! ማቆያ እንዲሆነኝ ጋዜጣ እገዛ ነበር. ጎሽ! ባቡሩ ቆመ፡፡ ወረድ ስል አንድ መለዮ የለበሰ የባቡሩ ኩባንያ ሰራተኛ አመስዬ፣ አይውረዱ፣ ሁለት ደቂቃ ብቻ ነው ያለን» አለኝ
«Je mn fous!» አልኩትና ወረድኩ («ደንታ የለኝም!»)
አንድ Le Monde ጋዜጣና ሁለት ሳንድዊች ገዝቼ እስክመለስ
ባቡሩ ተነሳ። ሮጬ ለትንሽ ደረስኩበት::
ጋዜጣውን ኣንብቤ ሳልጨርስ ወደሷ አልመለስም፡፡ ሳገኛት ደሞ ሳንድዊች እሰጣታለሁ፡፡
እየሳቅኩ። ጭራሽ አለመቅናቴ እንዲገባት የክሩስቼቭና የኬነዲ የቤንቤላ ስም አለ፤ የቪየትናም ሁከት ተጠቅሷል፣ ግን በደምብ አልገባኝም፡ የሲልቪ ፈገግታ፣ ለሌላ ያሰራችው ፈገግታ አንጎሌን በጥብጦታል። የሆነ ሆኖ፣ ያልኩት ግማሽ ሰአት አለፈልኝ። ኧረ ሰላሳ ሶስት ደቂቃ ነው ያለፈው! እኔ የሰውዬው ልጅ! ... ወደኛ ሰረገላ አመራሁ ሲልቪ የለችም። ሰውዬውም የለም፡፡
የታባታቸውን ሄዱ? እንደገና ፈረንሳዮቹን እየገጨሁ «Pardon!»
እያልኩ አንድ አምስት ሰረገላ ካቋረጥኩ በኋላ፣ ራሴን «የት ነው
ምትሄደው?» አልኩት፡፡

ቆምኩ «በቁላህ ሳይሆን በጭንቅላትህ አስብ» የሚል ሀሳብ ውስጡን አሳቀኝ። ለመሆኑ፣ ባገኛቸውስ ምን ላደርጋቸው ኖሯል ብዬ አሰብኩ። ተመልሼ ቦታዬ ቁጭ ብዬ ልጠብቃቸው ቆረጥኩ፡፡
👍20
«እቺ ውሻ ከኤክስ አጣድፋ ያመጣችኝ ለዚህ ኖሯል? “ማን
መስያታለሁ'? ፈረንሳይ መስያታለሁ? አበሻ መሆኔን ማን በነገራት!ቆይ አሳያታለሁ ግን አልቸኩል። ዝግ ብዬ ረጋ ብዬ ሳስብ።እንደ ልጅ መጮህ መፍጨርጨር አያስፈልግም
እሷ አሁን አስቀናሁት ብላለች። እስቲ ማን ማንን እንደሚያስቀና እናያለን፡፡እቺ ቅሌታም ፈረንሳይ! ዋናው ነገር፣ እሁን እንዳልቀናሁ
ማሳየት ነው። ስትመጣ ልክ አንደ ድሮ አናግራታለሁ። ልክ
ባለሽበቱን ሰውዬ እንዳላየሁት መሆን አለብኝ፡፡ሌላ ቀን ታድያ፣ ከሁለት ወይ ሶስት ሳምንት በኋላ፣ መኖር እስኪያስጠላት
ድረስ አስቀናታለሁ። ያኔ እናያለን

እንዲህ የበቀል ሀሳብ እያሰላሰልኩ ወደ ቦታዬ በኩል ስራመድ፤መመላለሻው ዘንድ እያጨሱ፤ እያወሩ ወይም ፈዘው በመስኮቶቹ በኩል ወደ ውጭ እየተመለከቱ ከቆሙት ሰዎች አንዱ ከሩቅ ስመጣ
ጀምሮ ያየኛል ፀጉሩ ሳይ ሽብት ዘርቶበታል፤ ፊቱ ቀጭን ቆንጆ ብጤ ነው::አይኑ ሰማያዊ ባይሆንም ሽበቱና የቆንጆ ፊቱ መቅጠን አበሽቀኝ፡፡አጠገቡ እስክደርስ በብሩህ ቡናማ አይኖቹ ያየኛል። እየገላመጥኩት

«ምነው ያዩኛል?» አልኩት። እንደ መደንገጥ ብሎ

«ምንም መስየ» አለ

ፀጉርዎ አስር ጊዜ ሽበት ሲኖረው je men fous!» አልኩት።
(ደንታ የለኝም»)

ስለምን እንደማወራ አልገባውም፣ ግን ፈርቷል። ዝም አለ፡፡ሰውዬው ምንም እንዳልበደለኝና አሁን የማወርድበት ቁጣ ፈጽሞ
የማይገባ ጭቦ እንደሆነ ይሰማኛል፤ ግን ራሴን ለመግታት
አልቻልኩም፡፡ መልኩንና እድሜውን እያየሁ በንዴት ተቃጠልኩ

በሉ እንጂ ይንገሩኝ፡፡ ለምን ያፈጡብኛል? ሰው ሳንድዊች ይዞ
ሲሄድ አይተው አያውቁም? ወይስ ርቦዎታል? እንኩ ብሉት!»
አልኩና የያዝኩትን ሳንድዊች በድንገት አስጨብጨው ወደ ቦታዬ በኩል በንዴት ስራመድ፣ መተላለፊያው ውስጥ ያሉት ሰዎች ሁሉ በፀጥታ እኔን እንደሚመለከቱ ድንገት ታየኝ፡፡ ንዴቴ ወደ እፍረት ተለወጠ፤ ሽበታሙ ሰውዬ በጣም አሳዘነኝ፡፡ ይኸኔ'ኮ ወጣት ቢሆን
አይታገሰኝም ነበር፡ አሁን ወጣትነቱን በሀዘንና በናፍቆት ያስታውስ ይሆን? እረ ምን በደለኝና ነው ያዋረድኩት? መባለጌ በጣም ቆጫኝ፡፡ ቀኝ ኋላ ዞሬ ወደሱ ተራመድኩ። ሳንዲውቾቹ የተጠቀለሉበትን ወረቀት በሁለት እጁ እንደጨበጠ ይመለከተኛል። ፊቱ ላይ የመደናገር እንጂ የንዴት ስሜት አይታይም

መስዬ፡ እባክዎን ይቅርታ ያድርጉልኝ፡፡ ጤና አልያዘኝም
አልኩት። ታችኛ ከንፈሬ ሲንቀጠቀጥ ተሰማኝ ግን መንቀጥቀጡን አስተወው አልቻልኩም፡፡ ሲጨንቀኝ ጊዜ አፌን በእጄ ያዝኩት ረጋ ባለ ድምፅ “Ca ya jeune bornime. Yy perisons plus"
አለኝ። («ግድ የለም ጎበዝ። እንርሳው») “Merci, mossieur” ብዬው
ብሄድ ጥሩ ነበር፡፡ ግን አሁንም ራሲን ለመግታት ኣልቻልኩም፡፡
ሳልወድ በግድ ለፈለፍኩ
«ጤና ስላልያዘኝ ነው እንጂ ከገሬ ብሆን፣ እንኳን እኔው ራሴ ሽበት ያለው ሰው ልሰድብ፣ ማንም ወጣት እንዲህ ሲያደርግ ባየው
እጣላዋለሁ» አልኩት

«አውቃለሁ አለኝ»

«ያውቃሉ?»

የናንተን አገሮች ባህል በደምብ አውቀዋለሁ፡፡ ዩኒቨርሲቲ
ውስጥ የአንትሮፖሎጂ ፕሮፌሰር ነኝ፡፡ ደሞ፣ ካደጉበት አገር ወጥቶ
አንግዳ አገር ሄዶ፣ ባእድ ህዝብና ባይተዋር ባህል ሲያጋጥም፣
በመጠኑ ግር እንደሚል አውቃለሁ።ደጋግሜ ካገሬ ወጥቼ
አይቼዋለሁ። ስለዚህ አሁን እኔን ይቅርታ መጠየቅ በጭራሽ
አስፈላጊ አይደለም፡፡ ይልቅ ቡና ልጋብዝዎትና ትንሽ እንጫወት-
ብሉ ቡና ወደሚጠጣበት ሰረገላ ወሰደኝ ሰውዬው ሊቅ ከመሆኑም በላይ ብልህና ደግ ነበር። ኮኛክ እየጠጣን ሳንድዊቾቹን በላናቸው
«ከኮኛክ ጋር እንኳ ሳንድዊች አይበላም፡ ብቻ ግድ የለም አሉ
ሰውዬው እየሳቀ:: ብዙ ብዙ ወሬ አወራን፡፡ በተለይም ስለአልጄሪያ
ጦርነት በሰፈው ነገረኝ፡፡ ጀኔራል ደጐል ባይኖር ኖሮ፣ ይህን ጊዜ
ፈረንሳዮች በአልጄሪያው ሁከት ምክንያት እርስ በራሳቸው
ተከፋፍለው ተዋግተው ትፋጅተው፣ ፍራንስ ራሷ ገደል ገብታ ነበር፤ አለኝ፡፡ እስከ ፓሪሰ እያወራን ብንሄድ ደስታዬ ነበር። ግን ፕሮፌሰሩ ዲዦን ወራጅ ነበር

ሲለየኝ፣ መውረጃው በር አጠገብ እንደቆምን፣ ሳላስበው እጆቹን
ትከሻዬ ላይ አሳረፈና፣ ደግነት በተሞሉ የአዋቂ አይኖቹ እያየኝ፣
አንቱ ማለቱን ትቶ ለመጀመሪያ ጊዜ አንተ እያለኝ

“ይገርማል፡ ጠቆርክ እንጂ ልክ የመጀመሪያ ልጄን ነው የምትመስለው፡፡ እንግዲህ ልጄ ትዝ ባለኝ ቁጥር አስታውስሀለሁ። ትናፍቀኛለክ Enfin, c'est la vie. Au revoire, jeune homme" (ይህ ነው የኑሮ ነገር፡ በል ደህና ሁን፣ ጐበዝ) አለና፡ ፈረንሳዮቹ የሚወዱትን ሰው ሲሰናበቱ አንደሚስሙት ጉንጭና ጉንጬን ሳመኝ። በእጁ ራቅ አድርጎ በናፍቆት አይን አየኝ። ፀጉሬን በእጁ በተን በተን አድርጎ፣ እንደገና ሳብ አድርጉ በኃይል እቅፍ አደረገኝና፣ ከባቡሩ ወረደ። ሻንጣውን ሳቀብለው፣ አይኑ ውስጥ እንባ አየሁ

ባቡሩ ቀስ ብሎ ተነሳ፡፡ «ልጄ ትዝ ባለኝ ቁጥር» እንዳለኝ አስታወስኩ

ከባቡሩ በላይ ጮኬ
ልጅዎ የት ነው? » አልኩት
«ሞቷል። አልጄሪያ» አለኝ፣ እጁን የስንብት እያራገበ
እጀን ሳወዛውዝለት፡ ተሰምቶኝ የማያውቅ አይነት ሀዘን ልቤን
ሞላው። አልቅስ አልቅስ አለኝ፡፡ እዚያ ቆሞ እጁን ሲያወዛውዝልኝ፣
እየራቀና እያነሰ ስሄድ፡ በሀይል እሳዘነኝ። በመጨረሻ ከአይኔ
ተሰወረ። ምን ያህል እንደወደድኩት ገና አሁን ገባኝ ..

መሬት መሬቱን እያየሁ፤ ማንንም ሳልገጭ፣ በዝግታ ወደ ቦታዬ ሄጄ ቁጭ ኣልኩ፡፡ በመስኮት ወደ ውጭ እያየሁ በብዙ አዘንኩ፡፡ ሲልቪ ደጋግማ ታወሰችኝ፡ ግን ንዴቱ ለቆኛል። ቅድም አሰላስል የነበረው የበቀል ህሳብ ከንቱ ሆኖ ታየኝ፡፡ ምስኪን ሲልቪ!
አሁን ምን አጠፋች? ካንዱ ጋር ስላወራች ነው? ታድያ ያገራቸው
ባህል ነው:: ደሞ ባህላቸው ባይሆንስ ምን አለበት? አሁን ባቡር ውስጥ ምን እንዳያደርጉ ነው?. .. ኧረ የፈለጉትንስ ቢያደርጉ ምን እንዳይቀርብኝ ነው?

ሰዎቹ ሻንጣቸውን ከተሰቀለበት ማውረድና መተራመስ ጀመሩ። ፓሪስ መድረሳችንም ነው። ሲልቪ ከሄደችበት ተመለሰች
ሰውዬው ግን አልመጣም) ሻንጣዋን አወረድኩላት። እንዴት እንደም ታናግረኝ ጨንቋታል። ምን አንደሆነ እንጃ፡ በጣም አሳዘነችኝ፡፡አቅፌ አይዞሽ ልላት ፈለግኩ፡፡ ግን ጊዜውም ቦታውም አይፈቅድም
«በለይል ርቦኛል። አልራበሽም?» አልኳት እየሳቅኩ። ያ ሳቅ ፊቴ ላይ ምን እንደሚመስል ብቻ እግዜር ይወቀው

«አዎን፣ በሀይል ርቦኛል» አለች

«ነይ፣ እራትሽን ላብላሽ” አልኳት

ከባቡር ጣብያው ትርምስምስ ወጥተን፣ እዚያው አጠገብ ኣንድ
ያረጀ ብጤ ሆቴል ውስጥ አንድ ክፍል ተከራይተን፣ ገላችንን
ታጥበን፣ እዚያው ሰፈር አንድ ርካሽ ብጤ ምግብ ቤት ውስጥ ጥሩ እራት በላን፡፡ ከሶስት ጠርሙስ ቀይ ወይንና፣ ከብዙ ብዙ ወሬ በኋላ፣ ሁለታችንም በጣም ሞቅ ብሎን ሳለ፣ እጄን ይዛ በቆንጆ ሰማያዊ አይኖቿ እያየችኝ

«ትፈልገኛለህ?» አለችኝ። የቀኑ ንዴት እሁንም ልቤ ውስጥ
አንድ ጊዜ ተገላበጠ፡፡ ግን በጭራሽ እንዳልተበሳጨሁ ማስመሰል አለብኝ በማለት፤ ጥቁር ፀጉሯን እየዳበስኩ

በሀይል በሀይል እፈልግሻለሁ» አልኳት። እውነቴን ነበር፡፡

«ና ቶሎ እንሂድ» አለችኝ.
👍151👏1
እንግዲህ እኔና ሲልቪ ስንተቃቀፍ በመብራት እየተያየን እያወራን፣ እየሳቅን ነው:: ዛሬ ግን ኣልጋ ውስጥ ስንገባ መብራቱን
አጠፋችው፣ በጭለማው ስታቅፈኝ ያለልማዲ ቸኮለች፡ ተንገበገበች።
አንድ ቃል አልተናገረችም፡፡ በጭለማው እየሳመችኝ ማቃስት ብቻ ሆነ፡፡ ደስታው መሀል ላይ እንደደረስን፣ ያለልማዷ ከንፈሬን ነክሳ አሳበጠችኝ። ጠረኗ ብቻ የራሷ ሆነ እንጂ፣ እግር አነሳሷ ሳይቀር ተለወጠብኝ፤ በጠቅላላው ከሌላ ሴት ጋር እንደመተኛት ያህል ነበር።
መጨረሻ ላይ፣ በሀይል እየተንቀጠቀጠች፤ ፊቷን አንገቴ ውስጥ ቀብራ

«Oh piti monsieur! Pitié! Pitie!» እያለች አጉረመረመች።
(«አይ! ይማሩኝ፣ እባከዎን ይማሩኝ! ይማሩኝ!»)

ከጨረስን በኋላ ማልቀስ ጀመረች፡፡ ከዚህ በፊት አልቅሳ
አታውቅም፡፡ ተመስገን ሲያስጠነቅቀኝ፣ አንዳንዴ ነገሩ ካለቀ በኋቁ አይዞሽ የኔ ቆንጆ፣ ምን ሆነሻል?» እያልኩ ሳቅፋት
በሹክሹክታ
«አሁን አንተ ነህ የተኛኸኝ በሀሳቤ ግን ሌላ ሰው ነበር የተኛኝ፡፡ በጭለማው አንተ እያቀፍከኝ፣ ሌላ ሰው ሲያቅፈኝና ሲስመኝ ነበር የሚታየኝ። ገላዬን የሰጠሁት ለሌላ ሰው ነበር»

ስካሬ ባንዳፍታ ጠፋ
«ለዚህ ነው መብራቱን ያጠፋሽው?» አልኳት፡፡
«አዎን»
«አሁን እናብራው?»
«የለም እፈራለሁ። አሁን አይንህን ማየት አልችልም» ብላ
ተጠመጠመችብኝ
«እሺ ይቅር። አይዞሽ፣ አይዞሽ. .. ግን እኔን ማፈርሽ ቂልነት
ነው። ይልቅ አስረጂኝ»
«እኔም ለራሴ አይገባኝማ!»
«ምስጢሩን አስረጂኝ ማለቴ አይደለም፡፡ አሁን ለምሳሌ
ስንተቃቀፍ ሳለን' በሀሳብሽ ውስጥ ምን ምን ተደረገ?. . . ንገሪኝ
አይዞሽ የኔ ሲልቪ»
«ያው ያደረግነው ነገር ነው የተደረገውስ፡ ብቻ. . .»
«ብቻ?»
«ሰውዬው አንተ አልነበርክም
«ማን ነበር?»
አፍራ ዝም አለች
«ያ ባቡር ውስጥ የነበረው ሽበታም ሰውዬ ነው?»
በሹክሹክታ አለችኝ። ምንም ቅናት አልተሰማኝም፡፡ ስጋዬ ስጋዋን ስለጠገበው ይሆን?

«አዎን። እባክህን ይቅርታ አድርግልኝ፡፡ ወድጄ አይደለም»
ይሆን? በጭለማው ከጐኔ አስነስቼ እላዬ ላይ አስተኛኋትና፣ ባንድ እጄ ጀርባዋን፣ በሌላው እጄ ፀጉሯንና አንገቷን እያሻሽሁና አይኗን እየሳምኩ

«አሁን ምን ይሰማሻል?» አልኳት
«እንደምትወደኝ ይሰማኛል»
«አውቀሻል፡፡ እንግዲህ ይቅርታ ምናምኑን እርሺውና፣ ስለዚህ
ነገር የተቻለሽን ያህል ግለጪልኝ»

«እሺ። በመጀመሪያ ሰውዬን ሳየው ትንሽ ደስ አለኝ»
እየሳቅኩ፣
«ውሸታም! በሀይል ነው ደስ ያለሽ» አልኳት
እሷም እየሳቀችና በሀይል እያቀፈችኝ
«አቤት እንዴት ነው 'ምወድህ! እባክህን አግባኝ! አውቃለሁ
ከውቃለሁ፡፡ አገርህ እጮኛ አለችህ:: ደሞ ባትኖርህም ጥቁርና ነጭ ሲጋባ ትርፉ ብስጭት ነው:: አውቃለሁ። ጋብቻውን እንርሳው»
«ንገሪኝ»
«ሰውዬው ደስ አለኝ»
«ስጋዊ ምኞት አሳደረብሽ»
«አዎን። በሀይል ተመኘሁት። ግን. . .»
«ግን ምን?»
«እሱ ራሱ በስጋው እንዲገናኘኝ ኣልፈለግኩም»
«እንግዲያውስ?»
«አንተ እሱን ሆነህ እንድትተኛኝ ነው የፈልግኩት»
«ትንሽ አብራሪልኝ»
«እሱ ነው ያማረኝ፡፡ ግን እሱ ራሱ ሲገናኘኝ አልፈቅድም፡፡
ኣንተ ብትተኛኝ ነው 'ምፈቅደው:: ግን አንተ ስትተኛኝ አንተን
ሆነህ አይደለም፣ እሱን ሆነህ ነው፡፡ የሱ ገላ ነህ»
«እሱ በገላዬ እንዲያቅፍሽ ነው
'ምትፈልጊው?»
«አውቀሀል»
«ነገሩን ብናለዋውጠውስ?»
«እንዴት?»
«እሱ የኔ እንደራሴ ቢሆንና፣ የሱን ገላ እያቅፍሽ ስለኔ
ብታስቢት
«ብጭራሽ አይሆንም»
«እሺ ቀጥይ»
ቀጠለች። ግን ምንም ሌላ አዲስ ነገር አልነገረችኝም፡፡ ያው
ነበር። አንድ ወንድ ያማራት ጊዜ፡ እሱ ራሱ ከሚተኛት ይልቅ
ስለሱ አያሰሰች ሌላ ወንድ ቢተኛት ትመርጣለች ገረመኝ። ግን ሊገባኝ አልቻለም። ሁለት ሰአት ያህል ከተወያየንበት በኋላ እንደገና ሞቅ አለኝና ጭኗን ማሻሸት፣ ሰፊ አፏን መሳም ጀመርኩ። አሁንም ያለ ልማዷ ተንገበገበች፣ በብዙ አቃሰተች፣ ጀርባዬ እስኪደማ ድረስ ቧጨረችኝ፡ስትጨርስ እየተንቀጠቀጠች፣ Ah vous alors!Quel homme!»
እያለች እጉረመረመች። («አይ አንቱ! አይ ወንድ!»)

ከኔ ጋር እንዳልሆነች እያወቅኩ ውስጥ ውስጡን ተቃጠልኩ፡
የኔን ገላ ተውሶ ሌላ ሰው እንደተኛት እያወቅኩ ውስጥ ውስጡን ጦፍኩ፡፡ ግን የሴት ገላ እንደዚያን ቀን ልቤን አጥፍቶኝ አያውቅም።በነጋታው አያለሁ፡ ለካ ሳይታወቀኝ አንገቷን ሶስት ቦታ ነክሼያት ኖሯል። ለሚቀጥሉት አምስት ቀናት ረዥም እንገቷ ዙሪያ ሻሽ ጠምጥማ መማር ግድ ሆነባት፡፡ ለጌጥ የለበሰችው ይመስል ነበር

በዚህ አኳኋን ከቅናት ጋር ተዋወቅኩ፡፡ ግን ቅናት ምን አይነት ግሩም ስሜት መሆኑን ለመገንዘብ ብዙ ሳምንት ወሰደብኝ. ..

በነጋታው ሲልቪ ቤቶቿ ዘንድ ዋለች፡ እኔ ፓሪስን በኦቶቡስና
በእግር ስዞር ዋልኩ። ማታ ሆቴላችን ተገናኘን። ሁለታችንም ደክሞን ስለነበረ፣ አልጋ ውስጥ እንደገባን እንቅልፍ ወሰደን፡፡ ሲነጋ ተነስተን ቁርስ በልተን ፓሪስን ዞርን። ምሳ በልተን ፓሪስን ዞርን፡፡ እራት በልተን ፓሪስን ዞርን። አያልቅም የፓሪስ ውበትና የሲልቪ ሳቅ ጨዋታ። ከሌሊቱ በስምንት ሰአት ሆቴላችን ተመለስን። ስንተኛ

«ፓሪስ እንዴት ቆንጆ ናት!» አልኳት
«ይገርምሀል፡፡ ባንተ አይን ሳየው ጊዜ ሌላ ፓሪስ አየሁ፡፡ ነገም
ስንዞር እንዋል?

«አመት ሙሉ እንዙር ብትይኝ ደስ ይለኛል።»

«አንድ ሳምንት ብቻ ነው ምንዞረው:: ከዚያ የት እንደምንሄድ ታውቃለህ?»
«የት?»
«ጄኖቫ፡፡ የክሪስቶፎ ኮሎምቦ ከተማ»
«እኔ አንድ ሺ ፍራንክ ብቻ ነው ያለኝ ልብ አርጊ»
«ግድ የለህም፡፡ እኔ ሁለት ሺ አምስት መቶ አለኝ»
«እሺ እንግዲያው»
«አሁን እቀፈኝ የድሮዋ ሳቂታ ሲልቪ ናት፡፡ ከትላንት ወዲያ ሌሊት የነበረውን ማቃሰት፣ ማልቀስና መናከስ አሁን ሳስበው ህልም መስሉ ተሰማኝ፡፡
እሷም ፈፅማ የረሳችው ትመስላለች። ብቻ ሳላውቅ አንገቷን የነካኋት እንደሆነ አይ!» ትላለች፡ ሁለታችንም እናስታውሳለን

ሮማ ከመሄዳችን በፊት ጄኖቫ ሶስት ቀን አደርን። ሁለተኛውን
ሌሊት በተለይ አስታውሳለሁ። እራት ከበላን በኋላ፣ አንድ ሲጋራ
የማይሽጥበት ቡና ቤት ገብተን ስናወራ ቆይተን፣ ሲጋራዋ ስላለቀባት ልገዛላት ወጣሁ
ስመለስ ከአንድ ረዥም ብሉንድ (ባለ ነጭ ፀጉር) ጎረምሳ ጋር
ትተያያለች፡፡ እሱ ቡና የሚቀዳበትን ባንኮኒ ተደግፎ ቆሞ ያያታል፡
ጥብቅ ያለ ጂንስ ሱሪና እጅጌው አጭር የሆነ ነጭ ሸሚዝ ለብሷል።እሷ ጠረጴዛችን ጋ ቁጭ እንዳለች ሽቅብ ታየዋለች፡ ውብ አይኖቿ ፊቱና ገላው ላይ ይንከራተታሉ። ትንሽ ከተያዩ በኋላ ሳቅ አለች፡
ጉልህ አይኖቿና ሰፊ አፏ የምኞት እስክስታ ይወርዳሉ ማማሯ
ኣይኔን አንዴ ወደ ጎረምሳው ጣል አደረግኩ፡ ጥርሱን ሳያሳይ ነው
ፈገግታ የሚልክላት። እሷን አየኋት፡ ቀያይ ከንፈሮቿን ለመግጠም ትሞክራለች፣ ፈገግታው ግን ሊፈለቅቃቸው ይፈልጋል፡ ታዲያ ከናፍሯ በሚያስጎመጅ አኳኋን ይርበተበታሉ፡፡ (ምኞቱ ሲያሳብጠኝ ተሰማኝ ታድያ ከፍርሀት ጋር ነው፤ ምክንያቱም የተመኘኋት ቀን ስለሆነች ብቻ ሳይሆን፣ ሰውየውን ስትመኘው ስላየኋትም ነው።
👍19👏1
ነው?)
ድንገት እጇ ወደ አንገቷ ሄደ። ያን ጊዜ የነከስኳትን አስታወስኩ። ፊቷ ቀስ ብሎ ደም ለበሰ፡ አይኖቿ ተርገበገቡ የሰውየውን አይን ለመሸሽ ወደኔ በኩል አየች ከኔ ጋር አይን ለአይን ተጋጠምን!
ቅናቱ ደረቴን ያሳምመኛል፡ ግን ምንም እንዳላስተዋልኩ ያህል
(አሁን አሁን ከውጭ እንደመጣሁ አስመስዬ) ወደሷ ሄድኩና
ተቀመጥኩ። ሰውየው ወደ ኋላዬ ሆነ፡፡ ሲጋራ አያቀጣጠለች
«ስንት ሰአት ነው?» አለችኝ «አምስት ተኩል፡፡»
እንደ መድከም ብሉኛል፡፡ ሄደን አልጋ ውስጥ ተጋድመን
እናውራ?» አለችኝ፡፡ ገብቶኛል። እሺ አልኳት። ስንሄድ ቃል
አልተናገርንም፡፡ የከፍላችንን በር ቆለፍኩት፣ መብራቱን አጠፋችው።
በፀጥታ ልብሳችንን አወለቅን አልጋ ውስጥ ገባን፣ ተቃቀፍን። እንደ አንድ ቀኑ ሌሊት ተንገበገበች፡ ስስማት አፌ ውስጥ እያቃሰተች ጭኖቿን ከመጠን በላይ ፍርክክ አድርጋ አቀፈችኝ፣ ደምበኛው ፍቅር ሳይሆን፣ ቆሻሻ ብልግና የምንሰራ መስሎ ተሰማኝ። የባሰ ቆሻሻ
እንዲሆን አማረኝ፡ ጭኖቿን የባሰውን በለቀጥኳቸው። ወደ
መጨረሻው ልንደርስ ስንል ወፈፍ አደረጋት፤ በሚያስደነግጥ
ሰሚያስቀነዝር ሹክሹክታ «አፌ ውስጥ ይትፉ!» አለችና፡ መላ አፈ
ጎርሳ እስኪያመኝ ድረስ ጠባችው.
ነቃሁ ለካ እኔም ወፈፍ አርጐኝ ያለሁበትን ረስቼ፣ በሀይል እቅፌ
ይዤያት መተንፈስ ተስኗታል። ለቀቅ አደረግኳት። ቁና ቁና
መተንፈስ ጀመረች እኔም ቁና መተንፈስ ጀመርኩ፡ ሁለታችንም
በላብ ታጥበናል፡፡ በጭለማው ከግርጌ ፎጣ ሳብኩኛ ግምባሯን
መሀል ጡቶቿን፣ ብብቶቿንና ሆዷን አደረቅኩላት፡ «Merci.” ብላ
ፎጣውን ተቀበለችኝ፤ እኔንም አደረቀችኝ ያን ጊዜውኑ እንቅልፍ ወሰደን...

💫ይቀጥላል💫
👍111👎1
#የማያልቅ_ስጦታ

የካብኩት እየተናደ
የገመድኩትም ሲበጠስ
ያደመቅኩት እየፈዘዘ
ያነጽኩት ሁሉ ሲፈርስ
ደመናው ፀሐይ ሆኖብኝ
በመንገዴ እየተሰጣሁ
ከእንስራው ውሃ ጠፍቶ
ላቤን ከጉንጬ እየጠጣሁ
የበደሉኝን ይቅር ለማለት
ራሴን በራስ እየቀጣሁ
“ማነው?” ስባል “እኔ” የምል
የሰው ጥፋት የምሸከም
በኔ ይለፍ የምዘምር
እስክጠፋ የማልደክም
ሳይታሰብ እንደ መና
ከላይ ወርዶ የሚያወፍር
ስላለኝ ነው ታላቅ እውነት
ስላለኝ ነው አንዳች ክብር
ያንቺ ፍቅር...!

🔘ሰለሞን ሳህለ🔘
👍105🔥1
#ልክ_በዛሬው_ቀን...

አበባ ባልሰጥሽ ለራት ባልቀጥርሽም
#የኔ_ወድሻለሁ
ባለሽበት ሆነሽ ባለሁበት ሆኜ
አብረን እንደሆንን ራሴን አሳምኜ
እራት እበላለሁ እራትሽን ብይ
ስጦታሽን እንቺ አበባሽን እይ

#የኔ_ወድሻለሁ...
ያለንበት ቦታ ለስላሳ ሙዚቃ
ሰማሽው አይደለ ላንቺ ይሁን በቃ
አውቃለሁ የኔ ሴት አውቃለሁ የኔ ዓለም
ቀይ መጸሀፍ እንጂ ቀይ ልብስ አትወጂም
ለራት የለበስሽው...
ሰማያዊ ቀሚስ ነጭ እስካርፍ ያለበት
ይሁን ደስ ብሎኛል ደምቀሽ እመሪበት

#የኔ_ወድሻለሁ...
ዘና በይ ፈገግ በይ
ባለሁበት ሆኜ ባለሽበት ሆነሽ
ብቸኝነት የለም የኔ ሆይ ልንገርሽ
ያሳቤን ስጦታ በይ አሁን ክፈቺው
አየሽው... ?
ወደድሽው... ?
የልቤ ትንፋሽ ነው በልብሽ ተንፍሺው

#የኔ_ወድሻለሁ!!!

🔘ሰለሞን ሳህለ🔘
👍8
#ቦግ_እልም !!


#በአሌክስ_አብርሃም


አንዳንድ ታሪኮች አሉ፣የማያስደስቱ ግን ምን በወጣኝ ብቻዬን መሸከሜ ተብሎ ለሌሎች የሚነገሩ ልክ እንደዚህ.…

አንዳንጅ ታሪኮች ደግሞ አሉ፡ እንኳን ለግጥም፣ ለእግዜር ሰላምታ አፉ የማይፈታለትን ሰው በሐዘን ኮርኩረው ገጣሚ የሚያደርጉ፣ ልክ እንደዚህ….

ብቸኝነት ማለት …
ብዞዎች መካከል
አንድ ሆኖ መገኘት ?
ብቸኝነት ማለት …
ለሕዝብ እየታዩ ደምቀው እንዳበባ፧
በራስ ማንነት ውስጥ መቅለል ከገለባ ?
ብቸኝነት ማለት …
የብዙሀኑ ቀልብ ወዶን ሲንሰፈሰፍ፣
ራስን ረግጦ ወደ ምንም ማለፍ ?
ብቸኝነት ማለት ...
ዘላለም የሚያስንቅ ረዥም ጨለማ፣
በነገ አምላኪዎች በተስፈኞች መሐል፣
ከፍ ብሎ መቆም በሰቆቃ ማማ።
ለኩሰው ለብቻ የትዝታ ኩራዝ
በትላንት ሰንሰለት ተቀይዶ መያዝ ?
ብቸኝነት ማለት …
በዝምታ ጀልባ ከባሕር እእምሮ፣
ትላንት ላይ መቆም ዛሬን ወዲያ አባሮ …
ብቸኝነት ማለት ...

ይህ ታሪክ ያስጠላል። በተለይ እኔ ስጽፈው ያስጠላል። ምክንያቱም በተቻለኝ አቅም ሁሉ እንዲያስጠላ
አድርጌ ስለምጽፈው ነው። ለምን ? ትንሽ እንኳን ላሳምረው ብሞክር ሀጢያት የሠራሁ ስለሚመስለኝ ።

ከዓመት በፊት ነው፣ ጓደኛዬ ደወለና "አብርሽ 'ሚስ ክሪስመስ' ሞተችኮ” አለኝ። በቃ እንዲህ ነው
ያለኝ። እውነቱን ለመናገር አዞረኝ። ትንፋሽ ሁሉ ነው ያጠረኝ። ስልኬ ከእጄ ላይ ሊያመልጠኝ ነበር።
"ክሪስመስ” ያላት ስምረትን ነው። እኔ እንኳን እትዬ ስምረት ነበር የምላት።

“አትቀልድ ባክህ” አልኩት። ቀልድ አለመሆኑ ግን ገና ድሮ ተሰቶኝ ነበር።

“ማሪያምን ! አሁን ራሱ ፖሊሶች ቤቷ መጥተው በሩን ሰብረው ገቡ፡፡ ሬሳዋን ወደ ምርመራ ሊወስዱ እያዘገጃጁት ነው፤ እኛም እዛው ነን” አለኝ በተጋነነ ድምፅ። የድምፁ መጋነን ጦር ሜዳ መሀል ሆኖ ጦርነቱን የሚዘግብ ጋዜጠኛ እንጂ የአንዲትን ሚስኪን ሴት ሞት የሚያረዳ ጎረቤቷ አይመስልም።አንዳንዱ ሰው መርዶም ይሁን የምሥራች ቀድሞ ስለተናገረ ራሱን ጀግና አድርጎ ይቆጥራል ልበል?ግራ ታጋባሁ፡፡ እትዬ ስምረትን መቼ ለታ አንድ የገበያ አዳራሽ ውስጥ የገና ዛፍ ገዝታ ስትወጣ አይቻት ነበር። እትዬ ስምረት…!!

መጀመሪያ ሥራ እንደያዝኩ አካባቢ ቤት ልከራይ ሳፈላልግ አንድ ቆንጆ ግቢ ውስጥ አንዲት ክፍል ቤት አገኘሁ። ደላላው አጣድፍ ካስገባኝ በኋላ ሒሳቡን ወስዶ ከዛ አካባቢ ጠፋ። በኋላ ስሰማ ባለቤቷ 'እብድ' ናት አሉኝ፡፡ እንደውም ከእኔ በፊት የነበረውን ሰው “ነገውኑ ቤቱን ለቀህ ውጣ ትለዋለች ሰውየው ችላ ይላታል፡፡ ማታ እንደተኛ የሆነ ጭስ ይሸተውና ከእንቅልፉ ሲነሳ ቤቱ በጭስ ታፍኖ እንደውም በሩ አካባቢ ነበልባል ይመለከታል። በርግጎ ከአልጋው ይነሳና መስኮቱን በርግዶ ከክፍሉ
ይወጣል፤ እርቃኑን። እትዬ ስምረት የጋዝ መያዣ ጀሪካን ይዛና በቀኝ እጇ ክብሪት እንደጨበጠች
የሚንቀለውን እሳት እየተመለከተች በስስ ፒጃማ መልአክ መስላ ቆማለች። ራሷ ናት ቤቱን እሳት የለቀቀችበት። እሳቱን በጎረቤት ትብብር አጥፍተው፣ ዕቃውን ሌሊቱኑ አውጥቶ፣ ሰውየው ጠፋ ጠፋ

ይኸው ከስንት ወር በኋላ ቤቱን አሳድሳ ለእኔ አከራየችኝ። ይሄን ታሪክ ስሰማ ደንግጬ ደላላውን
አፈላሰግኩና፣ “እንዴት እብድ ቤት ታስገባኛለህ አንተ?” ብዬ ጮኽኩበት።

“ባክህ ሰው ሲያጋንን ነው፤ ስምረት እብድ አይደለችም። በእርግጥ ትንሽ ወፈፍ ያደርጋታል። ምን ችግር አለው? ሰው ላይ አትደርስ” አለኝ።

“እንዴት ነው የተኛ ሰው ላይ ጋዝ አርከፍክፋ እሳት የምትለቅ ሴትዮ ሰው ላይ አትደርስም የምትለወ።

“እነሱን አትስማቸው፣ ሰዬው ተተናኮሏት ይሆናል…” ብሎ ብዙ ብዙ ነገር አወራኝና አሳመነኝ፡፡
ውይ ደላላ ሲባል ።

የግቢው ፀጥታ ያስፈራል። ዙሪያውን የበቀሉት ረዣዥም የፅድ ዛፍች ዕድሜ ጠገብ ስለሆኑ ቤቱ የቤተክርስቲያን ግቢ አስመስሎታል፡፡ ባለቤቷ እትዬ ስምረት ሲበዛ ውብ የሆነች እድሜዋ እስከ 40 የሚገመት ሴት ነበረች። ታዲያ ስትገባም ስትወጣም ሰው ሰላም አትልም። ምንንም ሰላም አትልም። ቤቷ እንግዳ አይመጣም። አንድ ግቢ እኔና እሷ ብቻ እየኖርን እኔንም ሰላም አትለኝም "ምን ያምበጣርራታል…” እያልኩ በውስጤ ስቦጭቃት ብዙ ወራት አለፉ። የቤት ኪራይ ካልሰጠኋት
አትጠይቀኝም ነበር። ማንንም ባስገባ ባስወጣ ግድ የላትም። ውኃ ፈሰሰ፣ መብራት በራ የለ ብቻ
መኖሬን የረሳች ሴት ነበረች። መኖሬን ስለረሳችው ነው መሰል እኔም አከራይ መኖሩን ረስቼ በነፃነት መኖሬን ተያያስኩት።

ግቢ ውስጥ ከእኔ ቤት ፊትለፊት ያለ አንድ የፅድ ዛፍ ከታች እስከ ላይ የገና መብራት ተጠምጥሞበታል ሁልጊዜ ማታ ማታ ይንቦገቦጋል። ለምን እንደዚህ እንደሚሆን ይገርመኛል። በዓልም ይሁን አዘቦት መብራቱ ከዛፉ ላይ አይነሳም። ዝናብና ፀሐይ እየተፈራረቀበት አለመቃጠሉም ይደንቀኛል። አንዳንዴ መበራቱ ቦግ እልም ሲል ግቢውን የአደጋ ቀጠና ቢያስመስለውም ለስላሳ ብርሃኑን ግን እወደው ነበር።

ሴትየዋ የምትኖርበት ግዙፍ ቪላ ሁልጊዜም በሩ ዝግ ነው፡፡ ሥራዋ ምን እንደሆነ እግዚአብሄር
ይወቅ። አንዳንዴ ዘንጣ ትወጣና በትልልቅ ፌስታሎች ብዙ ዕቃ ይዛ ትመለሳለች። ከዛ በሯ ይዘጋል።
ማታ ማታ በቤቷ መስኮት በኩል ከመጋረጃው ጀርባ ፈዘዝ ያለ የገና መብራት ዓይነት ረጋብሎ ሲበራና
ሲጠፋ ይታያል። ግቢ ውስጥ የቆመች አንዲት አዲስ መኪና አለች፣ ሰማያዊ፡ ሁልጊዜ ቅዳሜ ጧት ራሷ ታጥባታለች። መኪናዋን ግን ነድታትም አስነስታትም አታውቅም፡፡ እንደውም መኪናዋ ጎማ ሥር ሳር በቅሏል። ለአንድ ዓመት ያህል እዛ ቤት ስቆይ አንድ ቃል ተናግራኝ አታውቅም። አሁን ይሄን ማን ያምናል .…? ዝም ቄሱም ዝም፣ መጽሐፉም ዝም። ቤቱ፣ እርሷ እና ግቢው በአጠቃላይ ይጨንቃል።

አንድ ቀን ታዲያ አምሽቼ ወጀ ቤት ስገባ፣

"አብርሃም!” አለችኝ በረንዳ ላይ ቆማ እየጠበቀችኝ ነበር።

"አቤት….” ስሟ ጠፋብኝ። ደግሞ ልክ ጣረሞት እንደጠራኝ ነበር የደነገጥኩት።

"እንኳን መጣህልኝ፤ መብራት ተበላሽቶብኝ ነበር" አነጋገሯ በጭንቀት የተሞላ ስለነበር የሆነ ሰው የታመመባትና ድንገተኛ ክፍል ደውላ እባካችሁ ለነፍስ ድረሱልን” የምትል ያስመስላት ነበር።

"እሺ ምን ችግር አለው…" ብዬ ወደ ትልቁ እና ተዘግቶ ወደ ኖረው ቤቷ ገባሁ። ሁሌም ወደዚህ ቤት
ለመግባት እጓጓ ነበር። ከገባሁ በኋላ ግን ያየሁትን ነገር ማመን አልቻልኩም።

ሰፈው ሳሎን ውስጥ በትንሹ ሃያ የሚሆኑ ሰው ሠራሽ የገና ዛፎች ተደርድረዋል። ኮርኒሱን ሊነካ
ከደረስው ትልቅ ዛፍ፣ እስከ ትንንሽ ዛፎች ቤቱ ከዳር እስከዳር ተሞልቷል። ምን ይሄ ብቻ ግድግዳው እንደ ሸረሪት ድር የተወሳሰቡና የተለያየ መጠን ባላቸው የገና መብራቶች ተወርሯል። የቤቱ መብራት
በሙሉ እየበራ ስለነበር የተበላሸው የትኛው እንደሆነ ጠየቅኳት። ወደ መኝታ ቤቷ መራችኝ። ማመን አልቻልኩም። መኝታ ቤት ስፍር ቁጥር በሌላቸው የገና አባት አሻጉሊቶች ተሞልቷል። መልበሻዋ
ላይ የተቀመጠ የሚወዛወዝ ጌጥ ነገር በቀጭን የሚቅጨለጨል ድምፅ የገና መዝሙር ያወጣል።
ድምጹ ይጨንቃል።አንድ የገና መብራት ነበር የተበላሸባት። ስመለከተው ተቃጥሏል። ይህንኑ
ነገርኳት። ፊቷ ግርጥት ብሎ “
ሊሠራ አይችልም? እባክህ እርዳኝ አለችኝ። ስትናገር እንባ እየተናነቃት ነበር። ግራ ተጋባሁ። በጣም ርካሽ የሆነና ያን ያህል የሚያሳስብ የገና መብራት ይህን ያህል ለምን እንዳስጨነቃት ማወቅ አልቻልኩም።

“በቃ ተቃጥሏል … ባይሆን ያን ያህል የሚያስፈልግሽ ከሆነ ነገ ከስራ ስመለስ እገዛልሻለሁ አልኳት፡
👍18
“እሰይ የኔ ጌታ፣ እባክህ ጥሩውን መርጠህ ግዛልኝ፣ እጠብቅሀለው.…” ብላ ቦርሳዋን አነሳችና
ለማውጣት ስትከፋፍት እጆቿ ይንቀጠቀጡ ነበር። ሁኔታዋን ስመለከት እኔም ተረባበሸኩ። ቦርሳዋ ከእጇ ወደቀ። አነሳችው። ሦስት መቶ ብር አውጥታ ሰጠችኝ።

“ይበቃ ይሆን…?” አለችና አንድ መቶ ብር ጨመረችልኝ። ቦርሳዋ በጣም በብዙ ድፍን መቶ ብር፣
የተሞላ ነበር።

በቀጣዩ ቀን የተቃጠለውን የሚመስል ገዝቼላት መጣሁና ሰጠኋት። እየተጣደፈች ተቀብላኝ ወደ ውስጥ ገባች። አመሰግናለሁ እንኳን አላለችኝም። መልሱንም አልተቀበለችኝም፡፡ ክፍቱን በተወችልኝ በር ገብቼ መልሱን ጠረጴዛዋ ላይ አስቀምጬላት ወጣሁ፡፡

እዛው ጎረቤት ያለ ዓለማየሁ የሚባል ባለሱቅ ደንበኛዬ
አንድ ቀን አብረን ቆመን እያለ ይህቺ ሴት ትልቅ የገና ዛፍ ሊቆምጬ አሸክማ ስትገባ አየናትና በወሬ ወሬ ስለአከራዬ ታሪክ አወራልኝ።

“አከራይህ … ትንሽ አእምሮዋ ንፋስ ሰርቋል …” አለኝ።

“እንዴት… " አልኩት ለወሬ ጓጉቼ።

"እየውልህ፡እትዬ ስምረት በጣም አሪፍ ሴት ነበረች፡፡ገና መኪናዋ ብቅ ሲል የሰፈር ሕፃናት ይንጭጫሉ፥ደግ ናት፣ የደግ መጨረሻ። ሰውን ሁሉ ማብላት ማጠጣት ነበር ሥራዋ፤ የዛሬን አያድርገውና። ደግዋ ባልዋ ከሷ የባሰ መልአክ ነበር መላጣ ነው ረዥም ሳቁ ብቻ የሚያጠግብ ፍቅራቸው ለብቻው ነው። በቃ ሲገቡ ተቃቅፈህ፣ ሲወጡ ተቃቅፈው፣ ሁልጊዜ ሙሸራ ነበር የሚመስሉት።እሷም ቆንጆ ነበረች።

ባላሱቁ ነገር ያረዝማል…

"..እናልህ የዛሬ እስር፣ አስራ ሁለት ዓመት አካባቢ ይሆናል። እትዬ ስምረት እርጉዝ ነበረች በቃ
የእነሱን ልጅ አይተን የሁለት ቆንጆ ባልና ሚስት ልጆች እያለ ጎረቤቱ ሲያወራ፤ መቼም የሰው አፍ
ክፉ ነው፣ ምን እንደሆነ ሳይታውቅ ባለቤቷ ራሱን ሰቅሎ ተገኘ።”

“ምን…!” አልኩት ደንግጬ።

“አዎ…ግቢያቸው ውስጥ ያለ ዛፍ ላይ ራሱን ሰቅሎ ተገኘ። እንደውም እትዬ ስምረት አስካሁንም ዛፉ ላይ የገና መብራት አድርጋበታለች። አላየሁትም እንዳትል ብቻ እዛው እየኖርክ” አለና ጫቱን በጥርሱ
ቀረጣጥፎ ወሬውን ቀጠለ ..

"እትዬ ስምረት ራሷን ስታ ሆስፒታል ገባች። ለቀብሩ እንኳን አልነቃችም ነበር። ያረገዘችውም ልጅ አስወረዳት። ከዛ በኋላ በቃ ይሄን ሁሉ ዓመት ሰው ሰላም አትል፤ ከሰው አትደባለቅ፣ የገና ዛፍ
እየሰበሰበች ግቢዋን ዘግታ መኖር ነው። ድንገት ከተነሳባት ከግቢዋም ልታባርርህ ትችላለች” አለና ፈገግ አለ።

"ዘመድ የላትም እንዴ” አልኩት።

“ሞልቷት ! ያውም የናጠጡ ሀብታሞች። እንትን ነዳጅ ማደያ የአባቷ ነው፣ ምንትስ ሱፐርማርኬት የወንድሟ ነው፣ ምንትስ አስመጪም የባሏ ነበር አሁን ቤተሰቦቿ እያስተዳደሩ ብር ለእሷ እንደፈለገች ይሰጧታል። ባይሰጧትም ስጡኝ አትልም። ሰው ስለማትፈልግ ማንም ቤቷን አይረግጥም። ብዙ ተጥሮላት ነበር። ፀበልም ወስደዋት ነበር። አማኑኤልም ወስደዋት ጤነኛ ናት ጊዜ እያለፈ ይሻላታል አሉ፤ ይሄው እሷ እንዳለች አለች ፤ አንዴ አለመለከፍ ነው አብርሾ …።" አለና ወደ ጫቱ ዞረ።

የነገረኝ ታሪh ወትሮም የሚቀፈኝን ግቢ እንዲከብደኝ አደረገኝ። እየቀፈፈኝ ወደ ቤት ስገባ ግቢው
ከነተለመደ ዝምታው ጋር ጣረሞት ሰፍሮበት ጠበቀኝ፡፡ ከቤቴ ፊት ለፊት ያ ቀፋፊ ዛፍ ዮገና መብራት
እንደ እባብ ተጠምጥሞበት ቦግ እልም ይልበታል። በጨለማው ውስጥ ዛፉ ላይ የተሰቀለ ሰው በቀስታ የሚወዛወዝ መስሎ ታየኝ ረዥም መላጣ ሰው…።

አንድ ሌሊት የስው ለቅሶ ሰምቼ ከእንቅልፌ ነቃሁ። ስቅስቅ ብላ የምታለቅ ሴት ነበረች። ጆሮዬ
ቆመ። በእርግጥም የሴት ለቅሶ ነበር። ክረምት ነው፣ ስስ ካፊያ ነበር። ቀስ ብዩ ከአልጋዬ ተነሳሁና
መጋረጃዬን ገለጥ አድርጌ ተመለከትኩ። እትዬ ስምሪት ባሏ የተሰቀላሰት ዛፍ ስር ቆማ በዚያ
ባሚያንዘፈዝፍ ካፊያ ስስ የውስጥ ልብስ ብቻ ለብሳ ታለቅሳለች። ጨነቀኝ፡፡ ወጥቼ አይዞሽ ልላት
ፈለግኩ፤ ግን ደግሞ ፈራኋት። አለቃቀሷ አስፈሪ ነበር፤ ኡኡታ ! ኩርምት ብላና ጡቶቿን በእጆቿ
እቅፋ ካፊያው እየወረደባት ትንሰቀለቃለች። ሰዓት ተመለከትኩ፣ ከሌሊቱ 10፡00 ሰዓት። ቦግ ኦልም ..ቦግ እልም ቀይ፣ አረንጓዴና ቢጫ ቀለማት ያሉት መብራቶች እቺን ሚስኪን ኮከብ በደረቅ ሌሊት ካፈያ ላይ የብርሃን መልኩን ይረጭባታል፡፡

እትዩ ስምረት ስታሰቅስ ካየኋት ከአራት ወር አካባቢ በኋላ ማታ ላይ በሬ ተንኳኳ። እሷ ነበረች።

"አብርሃም ደህና አመሸህ?”

“ደህና አመሸሽ እትዬ…"

“ቤት ፈልግና በዚህ ሳምንት ቤቴን ልቀቅ” ብላኝ ተመልሳ ወደ ቤቷ ሄደች።

ምንም አልተቀየምኳትም።

እንዲያወም አዘንኩ።

ብጠቅምም ባልጠቅምም እዚህ አስፈሪ ግቢ ውስጥ እኔ መኖሬ ለእሷም ጥሩ ነበር። ዝም ብዬ ሳስበው፣ ብቻዋን በዚህ ግቢ ውስጥ…አሰቃቂ ነገር ነው። ለማንኛውም በዛው ሳምንት ቤቱን ለቅቄ ወጣሁ። ቀስ በቀስም እትዬ ስምረት ከአእምሮዬ ደበዘዘች፡፡ ቤቱን ከለቀቅኩ ከአንድ ዓመት በኋላ እትዩ ስምረት መሞቷን ሰማሁ፡ ሞታ የተገኘችው ባለቤቷ የተሰቀለበት ዛፍ ስር ነበር - በስስ የውስጥ ልብስ ብቻ!አስከሬኗ ተመርምሮ ምንም ሕመም የለባትም፤ የሟቷ ምክንያት ግልፅ አይደለም ተባለ አሉ።

ቀብሯ ላይ ሄጄ ነበር። የተሰለፈ መኪና፣ ያልተያዘ የእትዬ ስምረት ፎቶ አልነበረም። የባሏም ፎቶ
ሲለቀስበት አይቻለሁ። ቤተሰቦቿ ከምር አሳዝነውኝ ነበረ። ከዛን ጊዜ ጀምሮ የገና ዛፍ፣ የገና መብራት
በተለይ የገና አባት የሚባሉትን አሻንጉሊቶች አልወዳቸወም !
ቦግ እልም ..ቦግ እልም ...ሰው ልጅ ገናው ፍቅር ነው። ቦግ ሲል መፋቀር በደስታና በተድላ መኖር።
ፍቅር እልም ሲል በቁም አልያም የማይቀረውን ሞት እንደወረደ መሞት። ቦግ..እልም፣ ቦግ እልም!!.....

አለቀ
👍173