#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንትዋብ ከተንሴ ማሞ ጋር በተደረገው ውጊያ በእሱ ሆነ በእሷ በኩል ያለቀው ሰው ብዛት በአእምሮዋ እየተመላለሰ እያደር ሰላም ነሳት። ሰላም በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ይበልጥ እንድትገነዘብ አደረጋት። ሰላምን በሃገሯ ውስጥ ለማረጋገጥ
የበለጠ ጠንክራ መስራትና የልጇን መንግሥት ማደላደል እንዳለባት
የበለጠ ተገነዘበች፤ የበለጠ ተጋች።
የልጇን መንግሥት ለማጠናከር ወልደልዑልን፣ ተንሴ ማሞን ባሸነፉ በዓመቱ ራስ ቢትወደድ ብላ ሾመችው። አፄ ፋሲለደስ ያሰሩት የራሶች መኖሪያ ራስ ግንብ ውስጥ እንዲገባ አደረገች።
ያሰበችውን ሁሉ ለማሳካት፣
ዘወትር ጠዋት አስራ ሁለት ሰዐት ላይ ዳዊቷን ደግማ የጸሎት መጽሐፏን አንብባ እንደጨረሰች ወይዛዝርት ልብሷን ያለብሷታል
ያስጌጧታል። ብሎም ቁርስ ታደርጋለች። አፈ ንጉሡ መጥቶ ፍትሕ ፈላጊ እንዳለ ካስታወቃት፣ ሦስት ሰዐት ላይ ዙፋን ችሎት ከኢያሱ ጋር ተሰይማ አቤቱታ ትሰማለች። ፍትሐ ነገሥት
ጠንቅቀው ከሚያውቁ መሃል የተመረጡት ዐራት አዛዦች ፍትሓ
ነገሥት እየጠቀሱ ፍርድ ሲያሰሙና ፍርዳቸውን ሲሰጡ ትሰማለች።መኳንንቱ አንድ በአንድ የሚሰጡትን የብይን ሐሳብ ታዳምጣለች።በመጨረሻም የተለየ የተለየ ፍርድ ካላት ትሰጣለች።
ሽንጎ እንደተነሳ እልፍኟ ትመለሳለች። ከልጇ ጋር ሆና መሣፍንት መኳንንትና ሌሎችም እጅ ይነሳሉ። እነሱን እንዳሰናበተች ዘወትር ለራሷ የምታቀርበው ጥያቄ እንዴት ላስተዳድር?” በመሆኑ ጉባኤ ጠርታ የልጇን መንግሥት ለማጽናት፣ ዘላቂ ሰላም ለማምጣትና ለሃገሯ
ያሰበችውን ለመሥራት፣ ያንገራገረ መኰንን ካለ ከጥል ይልቅ ዕርቅ
እየመረጠች ለዕርቅ ትደራደራለች።
ጥምረት መፍጠር ካለባት ጋር ጥምረት ትፈጥራለች፣ በጋብቻ
ማስተሳሰር ያለባትን ታስተሳስራለች፤ ማን ከማን ጋር መጋባት እንዳለበት ትወጥናለች። ብሎም የመሣፍንቱንና የመኳንንቱን ቀልብ መሳብ ብቻ ሳይሆን ድጋፋቸውንም አገኘች። ሊቃውንት አድናቂያቸው
ካህናት ደግሞ አክባሪያቸው በመሆኗ ሊፃረሯት ምክንያት አጡ።ደከመኝ፣ ታከተኝ ሳትል ያለ ዕረፍት ራሷን በሥራ ጠመደች።
ሙሉ ለሙሉ ለሃገሯ ሰላምና ደሕንነት ማሰቧ፣ ለልጇ ሕይወት መጨነቋ፣ ከተንሴ ማሞ ጋር የተደረገው ውጊያ ያሳደረባት ድካም፣ ተጽዕኖና ያለ ዕረፍት መሥራቷ፣ ስለ ራሷ የምታስብበት ጊዜ እንዳይኖራት አደረጋት።
በሏ ከሞቱ ሦስት ዓመታቸው ነው
አፍላ እድሜዋ ላይ
በመሞታቸው የልጅነት ጊዜዋ እንደዚሁ መጥፋቱ ክፉኛ አሳሰባት።ሕይወቷ ጨው ጎደለው፤ ድግስ ላይ እንደሚቀርበው አዋዜ፣ ድቁስና
የተሰነገ ቃርያ ማጣፈጫ አጣ። ቋራን ለቃ ቤተመንግሥት የገባች ቀን ሕይወት የፈነጠቀችላትን ብርሃን መልሳ እንደ ክረምት ሰማይ ግራጫ ያለበሰችባት መስሎ ተሰማት።
ሙሉ ፀጋዋንም ሰስታ የያዘችባት መሰላት።
ዳግማዊ ኢያሱ በትምህርቱ ጎበዝ፣ በቅኔ ትምህርቱም ብስል
አእምሮውን እያሳየ ቢመጣም፣ ከቤተመንግሥት ውጭ ወጥቶ መዘዋወርዐእና እንደማንኛውም ልጅ መጫወት በመፈለጉ ወደ ውጭ በወጣ ቁጥር
ምንትዋብ ነፍስና ስጋዋ ይላቀቃሉ። ጠባቂዎች ቢኖሩትም፣ ምንትዋብ
ክፉ ያሰበ ይገድልብኛል ብላ ስለምትሰጋ ከእሷው ጋር ካልሆነ ባይወጣ ትመርጣለች። የኢያሱ የተፋጠነ ዕድገት የደስታ ምንጭ ቢሆንላትም፣ ደጅ ደጁን ማለቱ ግን ተጨማሪ የጭንቀት መነሻ ሆኖባታል።
በዕረፍት ጊዜዋ ከተወሰኑ መኳንንትና የኣፄ በካፋ እህት
የወለተእስራኤል ልጅ ከሆነው ከኢያሱና ከካህናት ጋር ጨዋታ
ባትይዝ ኖሮ ሕይወት የበለጠ እየከበደችባት በመጣች። በተለይም ልዑል ኢያሱ ዘወትር ጠያቂዋ በመሆኑ የቅርብ ወዳጅ እየሆነ መጣ።
ዙርያዋን ከከበባትና ዘወትር ለሥልጣንና ለሹመት ከሚቁነጠነጠውና ከሚወዳደረው፣ ካባውን እያወናጨፈ ከሚከራከረው ባላባት ጎን እሱን ረጋ ብሎ ማየቷ አረጋጋት። ጨዋታው ደስ እያላት መጣ። ለስለስ ማለቱና ቁጥብነቱ ማረካት።
እቴጌ መሆን ታላቅ ነገር ነው። በአደባባይና በሸንጎ የምትታየው
ደርባባዋ፣ ጠንካራዋና ደስተኛዋ ምንትዋብ ግን መኝታ ቤቷ ስትገባ
ብቸኛ ነች። ልጇ ኢያሱ ስላደገ፣ ከእሱ ጋር አንድ መኝታ ቤት
መተኛቱን አቁመዋል ። መኝታ ቤቷ ስትገባ ክፍሉ ባዶ፣ አልጋዋ
ቀዝቃዛ ሆነው ይጠብቋታል። በተለይም ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሐሳቡ፣ ጭንቀቱና መጠበቡ በርትቶባታል።
አንድ ማታ ነው። ሁለተኛ ደርብ ላይ ባለው መኝታ ቤቷ መስኮት
ውጭውን ትመለከታለች አንዳንዴ ከራሷ ጋር ለመሆን ስትፈልግ
እንደምታደርገው። መንፈሷ ከመቼውም ጊዜ የበለጠ መረጋጋት አቅቶታል። ድፍን ጨለማው ላይ አፍጣ ቆየች። ለወራት ሲያስጨንቃት
የነበረው ሐሳብ ቀስ በቀስ ጭንቅላቷ ውስጥ ተንሸራቶ ገባ። እስተመቸ ብቻየን እቀመጣለሁ? የሚሉት ቃላት ከአፏ አፈትልከው ወጡ።ደነገጠች። የሰማት ሰው እንዳለም ለማወቅ በመስኮቱ ወደ ታች አየች።በአካባቢው ማንም ያለ አይመስልም።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስታወጣ ስታወርደው የነበረ ነገር ቢሆንም፣
እንደዚህ ከአፌ ይወጣል ብላ አልገመተችም። ነገሩን ዳግም ላታነሳ ከራሷ ጋር ቃል ተገባብታና አፍና የያዘችው ነገር ከአፏ አምልጠ ሲወጣ ተገረመች። መልሳ ስውር ወደ ሆነውና ምሥጢር ደብቆ ወደ እሚያስቀምጠው የሰውነቷ ክፍል ሰግስጋ ልታስገባው ሞከረች።
አዳምጭኝ እያለ የሚወተውተውን ድምፅ ግን ማስቆም አቃታት።
አወጣች፤ አወረደች። መፍትሔ እንደሌለው ተገነዘበችና በትካዜ ሄዳ አልጋዋ ላይ ጋደም አለች።
ጸሎት ልታደርስ ፈልጋ የጸሎት መጽሐፉን ከዕንጨት የተሠራውና
ከፊት ለፊቱ የመስቀል ቅርጽ ያለው ረጅሙ #አትሮኖሷ ላይ አጋድማ፣ ከአንዱ ጸሎት ወደ ሌላው ብታልፍ መንፈሷ አልረጋጋ አለ። ዛሬስ እዝጊሃር ይቅር ይበለኝ ጠሎቱም እምቢየው ብሎኛል። ገና ግዝየ ነው ዛዲያ ምን ልሥራ? ብላ ጋደም እንዳለች አካሏ በሥራ፣ ስሜቷ በሐሳብ ደክመው ነበርና እንቅልፍ ጣላት።
በጣሙን ያስደነቃትን ሕልም አየች።
እጅም፣ እግርም፣ ፊትም ሆነ ጭንቅላት የሌለው፣ ግን ባያሌው
ደስ የሚል፣ ብርሃን የተሞላው፣ ቀይ አበባ መሳይ ነገር የሚያናግራት ይመስላታል ።
“ምንትዋብ!”
“አቤት! አንተ ማነህ?”
“እኔ ፍቅር ነኝ። ፍቅር ታቂያለሽ?”
“አዎን፣ በልዥነቴ ጥላዬ ሚባል ልዥ ኋላም ባሌን አፈቅር ነበር።”
“ጥላዬ ኻይንሽ ስለራቀ ኸልብሽ ርቋል። ባልሽን ትወጂ ነበር።
ለፍቅር ገና ነበርሽ።”
“ፍቅር ምንድርነው?”
“እኔ አልገለጥም። ሕይወታችሁ ውስጥ ኻሉ ምሥጢሮች አንዱ ነኝ።እናንት ሰዎች እኔን ሙሉ ለሙሉ ማወቅ ስለተሳናችሁ እኔን ሊገልጹ ሚችሉ በቂ ቃላት አላደራጃችሁም። እኔን ትመኛላችሁ፣ ግና ነፍሳችሁ
ምትላችሁን አታዳምጡም። ጠቢቡ እንዳለው የመውደድ ቦታው ነፍስ ነው። ዛዲያ እኔን ለመሸከም ነፍሳችሁን ማዳመጥ ይጠይቃል።”
“እንዴ አሁን እኔ ኸልዤና ካገሬ የበለጠ ማፈቅረው አለ?”
“አየሸ ምንትዋብ እኔ አንድ ነኝ። እናንተ ግና የፍቅር ዓይነት
እያላችሁ አስር ቦታ ትከፋፍሉኛላችሁ። ፍቅር ማለት ሕይወት ማለት ነው፤ ሞትንም ስንኳ በፍቅር ማሸነፍ ይቻላል። ግና ፍቅር ለናንተ ሲያልቅ ያልቃል... ሲያረጅ ያረጃል። ኻንዱ ቀንሳችሁ ለሌላው ታበዛላችሁ። ለምሳሌ አሁን አንቺ ለልዥሽና ላገርሽ ያለሽ ፍቅር ልብሽን በሙሉ ስለገዛ ራስሽን ችላ ብለሻል። ስለዝኸ ሕይወት ሙሉ ትርጉሟን ልትለግስሽ አልቻላት አለ። ጭንቀት ሲፈታተንሽ ውሎ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንትዋብ ከተንሴ ማሞ ጋር በተደረገው ውጊያ በእሱ ሆነ በእሷ በኩል ያለቀው ሰው ብዛት በአእምሮዋ እየተመላለሰ እያደር ሰላም ነሳት። ሰላም በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ይበልጥ እንድትገነዘብ አደረጋት። ሰላምን በሃገሯ ውስጥ ለማረጋገጥ
የበለጠ ጠንክራ መስራትና የልጇን መንግሥት ማደላደል እንዳለባት
የበለጠ ተገነዘበች፤ የበለጠ ተጋች።
የልጇን መንግሥት ለማጠናከር ወልደልዑልን፣ ተንሴ ማሞን ባሸነፉ በዓመቱ ራስ ቢትወደድ ብላ ሾመችው። አፄ ፋሲለደስ ያሰሩት የራሶች መኖሪያ ራስ ግንብ ውስጥ እንዲገባ አደረገች።
ያሰበችውን ሁሉ ለማሳካት፣
ዘወትር ጠዋት አስራ ሁለት ሰዐት ላይ ዳዊቷን ደግማ የጸሎት መጽሐፏን አንብባ እንደጨረሰች ወይዛዝርት ልብሷን ያለብሷታል
ያስጌጧታል። ብሎም ቁርስ ታደርጋለች። አፈ ንጉሡ መጥቶ ፍትሕ ፈላጊ እንዳለ ካስታወቃት፣ ሦስት ሰዐት ላይ ዙፋን ችሎት ከኢያሱ ጋር ተሰይማ አቤቱታ ትሰማለች። ፍትሐ ነገሥት
ጠንቅቀው ከሚያውቁ መሃል የተመረጡት ዐራት አዛዦች ፍትሓ
ነገሥት እየጠቀሱ ፍርድ ሲያሰሙና ፍርዳቸውን ሲሰጡ ትሰማለች።መኳንንቱ አንድ በአንድ የሚሰጡትን የብይን ሐሳብ ታዳምጣለች።በመጨረሻም የተለየ የተለየ ፍርድ ካላት ትሰጣለች።
ሽንጎ እንደተነሳ እልፍኟ ትመለሳለች። ከልጇ ጋር ሆና መሣፍንት መኳንንትና ሌሎችም እጅ ይነሳሉ። እነሱን እንዳሰናበተች ዘወትር ለራሷ የምታቀርበው ጥያቄ እንዴት ላስተዳድር?” በመሆኑ ጉባኤ ጠርታ የልጇን መንግሥት ለማጽናት፣ ዘላቂ ሰላም ለማምጣትና ለሃገሯ
ያሰበችውን ለመሥራት፣ ያንገራገረ መኰንን ካለ ከጥል ይልቅ ዕርቅ
እየመረጠች ለዕርቅ ትደራደራለች።
ጥምረት መፍጠር ካለባት ጋር ጥምረት ትፈጥራለች፣ በጋብቻ
ማስተሳሰር ያለባትን ታስተሳስራለች፤ ማን ከማን ጋር መጋባት እንዳለበት ትወጥናለች። ብሎም የመሣፍንቱንና የመኳንንቱን ቀልብ መሳብ ብቻ ሳይሆን ድጋፋቸውንም አገኘች። ሊቃውንት አድናቂያቸው
ካህናት ደግሞ አክባሪያቸው በመሆኗ ሊፃረሯት ምክንያት አጡ።ደከመኝ፣ ታከተኝ ሳትል ያለ ዕረፍት ራሷን በሥራ ጠመደች።
ሙሉ ለሙሉ ለሃገሯ ሰላምና ደሕንነት ማሰቧ፣ ለልጇ ሕይወት መጨነቋ፣ ከተንሴ ማሞ ጋር የተደረገው ውጊያ ያሳደረባት ድካም፣ ተጽዕኖና ያለ ዕረፍት መሥራቷ፣ ስለ ራሷ የምታስብበት ጊዜ እንዳይኖራት አደረጋት።
በሏ ከሞቱ ሦስት ዓመታቸው ነው
አፍላ እድሜዋ ላይ
በመሞታቸው የልጅነት ጊዜዋ እንደዚሁ መጥፋቱ ክፉኛ አሳሰባት።ሕይወቷ ጨው ጎደለው፤ ድግስ ላይ እንደሚቀርበው አዋዜ፣ ድቁስና
የተሰነገ ቃርያ ማጣፈጫ አጣ። ቋራን ለቃ ቤተመንግሥት የገባች ቀን ሕይወት የፈነጠቀችላትን ብርሃን መልሳ እንደ ክረምት ሰማይ ግራጫ ያለበሰችባት መስሎ ተሰማት።
ሙሉ ፀጋዋንም ሰስታ የያዘችባት መሰላት።
ዳግማዊ ኢያሱ በትምህርቱ ጎበዝ፣ በቅኔ ትምህርቱም ብስል
አእምሮውን እያሳየ ቢመጣም፣ ከቤተመንግሥት ውጭ ወጥቶ መዘዋወርዐእና እንደማንኛውም ልጅ መጫወት በመፈለጉ ወደ ውጭ በወጣ ቁጥር
ምንትዋብ ነፍስና ስጋዋ ይላቀቃሉ። ጠባቂዎች ቢኖሩትም፣ ምንትዋብ
ክፉ ያሰበ ይገድልብኛል ብላ ስለምትሰጋ ከእሷው ጋር ካልሆነ ባይወጣ ትመርጣለች። የኢያሱ የተፋጠነ ዕድገት የደስታ ምንጭ ቢሆንላትም፣ ደጅ ደጁን ማለቱ ግን ተጨማሪ የጭንቀት መነሻ ሆኖባታል።
በዕረፍት ጊዜዋ ከተወሰኑ መኳንንትና የኣፄ በካፋ እህት
የወለተእስራኤል ልጅ ከሆነው ከኢያሱና ከካህናት ጋር ጨዋታ
ባትይዝ ኖሮ ሕይወት የበለጠ እየከበደችባት በመጣች። በተለይም ልዑል ኢያሱ ዘወትር ጠያቂዋ በመሆኑ የቅርብ ወዳጅ እየሆነ መጣ።
ዙርያዋን ከከበባትና ዘወትር ለሥልጣንና ለሹመት ከሚቁነጠነጠውና ከሚወዳደረው፣ ካባውን እያወናጨፈ ከሚከራከረው ባላባት ጎን እሱን ረጋ ብሎ ማየቷ አረጋጋት። ጨዋታው ደስ እያላት መጣ። ለስለስ ማለቱና ቁጥብነቱ ማረካት።
እቴጌ መሆን ታላቅ ነገር ነው። በአደባባይና በሸንጎ የምትታየው
ደርባባዋ፣ ጠንካራዋና ደስተኛዋ ምንትዋብ ግን መኝታ ቤቷ ስትገባ
ብቸኛ ነች። ልጇ ኢያሱ ስላደገ፣ ከእሱ ጋር አንድ መኝታ ቤት
መተኛቱን አቁመዋል ። መኝታ ቤቷ ስትገባ ክፍሉ ባዶ፣ አልጋዋ
ቀዝቃዛ ሆነው ይጠብቋታል። በተለይም ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሐሳቡ፣ ጭንቀቱና መጠበቡ በርትቶባታል።
አንድ ማታ ነው። ሁለተኛ ደርብ ላይ ባለው መኝታ ቤቷ መስኮት
ውጭውን ትመለከታለች አንዳንዴ ከራሷ ጋር ለመሆን ስትፈልግ
እንደምታደርገው። መንፈሷ ከመቼውም ጊዜ የበለጠ መረጋጋት አቅቶታል። ድፍን ጨለማው ላይ አፍጣ ቆየች። ለወራት ሲያስጨንቃት
የነበረው ሐሳብ ቀስ በቀስ ጭንቅላቷ ውስጥ ተንሸራቶ ገባ። እስተመቸ ብቻየን እቀመጣለሁ? የሚሉት ቃላት ከአፏ አፈትልከው ወጡ።ደነገጠች። የሰማት ሰው እንዳለም ለማወቅ በመስኮቱ ወደ ታች አየች።በአካባቢው ማንም ያለ አይመስልም።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስታወጣ ስታወርደው የነበረ ነገር ቢሆንም፣
እንደዚህ ከአፌ ይወጣል ብላ አልገመተችም። ነገሩን ዳግም ላታነሳ ከራሷ ጋር ቃል ተገባብታና አፍና የያዘችው ነገር ከአፏ አምልጠ ሲወጣ ተገረመች። መልሳ ስውር ወደ ሆነውና ምሥጢር ደብቆ ወደ እሚያስቀምጠው የሰውነቷ ክፍል ሰግስጋ ልታስገባው ሞከረች።
አዳምጭኝ እያለ የሚወተውተውን ድምፅ ግን ማስቆም አቃታት።
አወጣች፤ አወረደች። መፍትሔ እንደሌለው ተገነዘበችና በትካዜ ሄዳ አልጋዋ ላይ ጋደም አለች።
ጸሎት ልታደርስ ፈልጋ የጸሎት መጽሐፉን ከዕንጨት የተሠራውና
ከፊት ለፊቱ የመስቀል ቅርጽ ያለው ረጅሙ #አትሮኖሷ ላይ አጋድማ፣ ከአንዱ ጸሎት ወደ ሌላው ብታልፍ መንፈሷ አልረጋጋ አለ። ዛሬስ እዝጊሃር ይቅር ይበለኝ ጠሎቱም እምቢየው ብሎኛል። ገና ግዝየ ነው ዛዲያ ምን ልሥራ? ብላ ጋደም እንዳለች አካሏ በሥራ፣ ስሜቷ በሐሳብ ደክመው ነበርና እንቅልፍ ጣላት።
በጣሙን ያስደነቃትን ሕልም አየች።
እጅም፣ እግርም፣ ፊትም ሆነ ጭንቅላት የሌለው፣ ግን ባያሌው
ደስ የሚል፣ ብርሃን የተሞላው፣ ቀይ አበባ መሳይ ነገር የሚያናግራት ይመስላታል ።
“ምንትዋብ!”
“አቤት! አንተ ማነህ?”
“እኔ ፍቅር ነኝ። ፍቅር ታቂያለሽ?”
“አዎን፣ በልዥነቴ ጥላዬ ሚባል ልዥ ኋላም ባሌን አፈቅር ነበር።”
“ጥላዬ ኻይንሽ ስለራቀ ኸልብሽ ርቋል። ባልሽን ትወጂ ነበር።
ለፍቅር ገና ነበርሽ።”
“ፍቅር ምንድርነው?”
“እኔ አልገለጥም። ሕይወታችሁ ውስጥ ኻሉ ምሥጢሮች አንዱ ነኝ።እናንት ሰዎች እኔን ሙሉ ለሙሉ ማወቅ ስለተሳናችሁ እኔን ሊገልጹ ሚችሉ በቂ ቃላት አላደራጃችሁም። እኔን ትመኛላችሁ፣ ግና ነፍሳችሁ
ምትላችሁን አታዳምጡም። ጠቢቡ እንዳለው የመውደድ ቦታው ነፍስ ነው። ዛዲያ እኔን ለመሸከም ነፍሳችሁን ማዳመጥ ይጠይቃል።”
“እንዴ አሁን እኔ ኸልዤና ካገሬ የበለጠ ማፈቅረው አለ?”
“አየሸ ምንትዋብ እኔ አንድ ነኝ። እናንተ ግና የፍቅር ዓይነት
እያላችሁ አስር ቦታ ትከፋፍሉኛላችሁ። ፍቅር ማለት ሕይወት ማለት ነው፤ ሞትንም ስንኳ በፍቅር ማሸነፍ ይቻላል። ግና ፍቅር ለናንተ ሲያልቅ ያልቃል... ሲያረጅ ያረጃል። ኻንዱ ቀንሳችሁ ለሌላው ታበዛላችሁ። ለምሳሌ አሁን አንቺ ለልዥሽና ላገርሽ ያለሽ ፍቅር ልብሽን በሙሉ ስለገዛ ራስሽን ችላ ብለሻል። ስለዝኸ ሕይወት ሙሉ ትርጉሟን ልትለግስሽ አልቻላት አለ። ጭንቀት ሲፈታተንሽ ውሎ
👍7
አደረ። የጎደለሽን አውቀሻል። ለምን እንደሆነ ግና ማወቅ አልሆነልሽም።እኔ ነግርሻለሁ፣ የመጣሁት ለዝኸ ነውና። አንቺ ሰላማዊና ለጋሥ ሰው ነሽ፣ ሰርክ ምትጨነቂው እንዴት እንደምታስተዳድሪ ነው። ይኸ ርግጥ ታላቅነትሽንና ለሌላው ያለሽን ፍቅር ያሳያል ። እንዴት ልኑር ብለሽ ባጠይቂም እንዴት ላስተዳድር ብለሽ መጠየቁ ራሱ እንዴት መኖር እንዳለብሽ ማወቅሽን ያመለክታል። ያወቅሽው ግን ለሌሎች ነው።
እነሱን ስለምትወጂ ለራስሽ ብታስቢ ኸነሱ ምቀንሽ መስሎሻል። አሁን እኔ የመጣሁት ለራስሽም ሆነ ለሌሎች ሚሆን ፍቅር ነፍስሽ መያዟን
ልነግርሽ ነው።”
“ርግጥ አሁን ሕይወቴ ጎደሎ ሆኖ ይሰማኛል። ማግባትና ልዥ
መውለድ ፈልጋለሁ። ኢያሱ ደሞ አገር ለማስተዳደር ዕድሜው
ገና ነው። እኔ ከጎኑ ሁኘ ማገዝ አለብኝ። ላገሬ ብዙ ለመሥራት ተስፋና ምኞት አለኝ። ለሌላ ነገር ግዝየ የለኝም። በዝኸ ላይ የንጉሥ ምሽት ነበርሁ። የንጉሥ ምሽት ደሞ ባሏ ሲሞት ማግባት አትችልም። እንዳው ላግባ ብየ ባስብ ስንኳ ይኸን ወግ እንዴት ብየ መጣስ ይቻለኛል?”
“ምንትዋብ! በሁለት ነገሮች መኻል እየዋዠቅሽ ነው። ባንድ በኩል የሕይወት አጋር ሚሆንሽ ትፈልጊያለሽ። በሌላ በኩል ላገርሽ ብዙ እልም ስላለሽ ሌላ ነገር ማረግ ምትችይ አልመሰለሽም። እናም ምንትዋብን ረሳሻት። ባሏ የሞተባት የንጉሥ ምሽት ሌላ ማግባት አትችልም ሚለውን ይትበሃል እንዴት መጣስ ይቻለኛል ለምትይው እሱ ማዶል ዋናው ችግርሽ። ለመሆኑ አንቺ ላልመሰለሽ ነገር ከመቸ ወዲህ ነው መጨነቅ የዠመርሽው? ዋናው ችግርሽ ሕይወትሽ ወደ አንድ ወገን.. ወደ ሥራ... ማዘመሙ... ሚዛን ማፋለሱ ነው። በዝኸ መኻል ነው ምንትዋብ የተጎዳችው። አየሽ የሰው ልዥ ጭንቅላት አንዱን የተፈጥሮ
ፍላጎቱን ችላ ብሎ ሌላውን ብቻ ይዞ መዝለቅ አይቻለውም። ይኸን
የጎደለበትን ማካካስ ሳይችል ሲቀር ችግር ውስጥ ይገባል። ጭንቅላት ተፈጥሮ ነውና ተፈጥሮ እንደምታደርገው ሚዛን መጠበቅ... ማካካስ አለበት ። አንቺም የጎደለውን እየሞላሽ ሚዛን እያስተካከልሽ ብትኸዲ
ሕይወትሽ የተቃና በሆነ።”
“እኔስ ግራ ገባኝ። እልም እያለምሁ ነው?”
“እያለምሽ ነው።”
“እያለምሁ ነው? እንግዲያማ ምን ፋይዳ አለው? እንደዝኸ ደስ
ሚል ነገር ነግረኸኝ እልም ነው ስትለኝ የሰጠኸኝን ተስፋ እየቀማኸኝ ማዶል?”
እየ ምንትዋብ! አስተዋይ ሴት ነሽ ግና ደሞ የዋህ ነሽ ። እልም
ፋይዳ የለውም ነው ምትይ? እልም እኮ አንዳንዴ ሚነግርሽ መልክት እንድትሞይ፣ ያዛባሽውን ሚዛን እንድታስተካክይ ላሳይሽ፣ ምልክት አለው። ሌላ ግዝየ ደሞ ያስጠነቅቅሻል። እኔ አሁን ያጎደልሽውን ልሰጥሽ ነው የመጣሁት።”
ያንን ካላት በኋላ፣ ያ ቀይ አበባ የመሰለ ነገር እየራቀና እየደበዘዘ
ሲሄድ፣ በምትኩ ኢያሱ - የአፄ በካፋ እህት ልጅ - ታያት። በነጭ
ተነፋነፍ ሱሪ ላይ ረጅም ነጭ ጥብቆ አድርጎ፣ ጥብቆው ላይ ነጠላ ለብሶ በላዩ ላይ ነጭ ካባ ደርቧል።
ኢያሱ... የወለተስራኤል ልዥ ... ኑሯል እንዴ ይኸን ሁሉ ሲለኝ
የነበረው? ስትል፣ ብንን አለች። ምን ያለ እልም ነው? ሲያቃዠኝ
ነው? አለችና አፏን ባንድ እጇ ይዛ ጣሪያ ጣሪያውን ተመለከተች።
ጉልህና ደስ የሚል ሕልም!
የሕልሟ ትርጉም ምን ሊሆን እንደሚችል መመርመር ጀመረች።
ቅዠት መሆን አለበት። የለም የለም ይኸ ቅዠት ማዶል... እልም
ነውና ... በገሀድ እያሳየኝ ውነት ነው ራሴን ጎድቻለሁ። ውነት ነው
ብቸኝነት እያጠቃኝ ነው። ዛዲያ ምን እያለኝ ነው? አግቢ? ባሌ
መተው ማግባት እንዴት ይቻለኛል? እንዴ ደሞ እረ ጉድ ነው
ኸሰው መኻል ኢያሱን ያሳየኝ ለምነው? አንድ ነገርማ አለ! እያለች ተገረመች።
የዛን ዕለት ጠዋት ኢያሱ ቤተመንግሥት እጅ ሊነሳ
ሲገባ ይኽ ሰው እንዲኽ መልከ መልካም ኑራል እንዴ? ያለችው ትዝ አላት።ምናልባትም እኮ እዝጊሃር ሊያመላክተኝ የፈለገው ነገር ይኖራል። ኸለዛ ኸሰው መኻል ስለምን እሱን በእልሜ ያመጣዋል? ነው አለወትሮየ
በእልሜ የመጣው? እያለች፣ አወጣች አወረደች። ተመልሳ ለመተኛት ሞከረች። እንቅልፍ አልወስድ ብሏት ስትገላበጥ ቆየች። ነገሩን የበለጠ
አሰበችበት፤ ከነከናት። እረ ስለምነው እንደዝኸ ለእልም መጨነቄ!ለዳግም ስለዝኸ ጉዳይ ማሰብ የለብኝም እያለች ስታሰላስል ነጋ።.....
✨ይቀጥላል✨
እነሱን ስለምትወጂ ለራስሽ ብታስቢ ኸነሱ ምቀንሽ መስሎሻል። አሁን እኔ የመጣሁት ለራስሽም ሆነ ለሌሎች ሚሆን ፍቅር ነፍስሽ መያዟን
ልነግርሽ ነው።”
“ርግጥ አሁን ሕይወቴ ጎደሎ ሆኖ ይሰማኛል። ማግባትና ልዥ
መውለድ ፈልጋለሁ። ኢያሱ ደሞ አገር ለማስተዳደር ዕድሜው
ገና ነው። እኔ ከጎኑ ሁኘ ማገዝ አለብኝ። ላገሬ ብዙ ለመሥራት ተስፋና ምኞት አለኝ። ለሌላ ነገር ግዝየ የለኝም። በዝኸ ላይ የንጉሥ ምሽት ነበርሁ። የንጉሥ ምሽት ደሞ ባሏ ሲሞት ማግባት አትችልም። እንዳው ላግባ ብየ ባስብ ስንኳ ይኸን ወግ እንዴት ብየ መጣስ ይቻለኛል?”
“ምንትዋብ! በሁለት ነገሮች መኻል እየዋዠቅሽ ነው። ባንድ በኩል የሕይወት አጋር ሚሆንሽ ትፈልጊያለሽ። በሌላ በኩል ላገርሽ ብዙ እልም ስላለሽ ሌላ ነገር ማረግ ምትችይ አልመሰለሽም። እናም ምንትዋብን ረሳሻት። ባሏ የሞተባት የንጉሥ ምሽት ሌላ ማግባት አትችልም ሚለውን ይትበሃል እንዴት መጣስ ይቻለኛል ለምትይው እሱ ማዶል ዋናው ችግርሽ። ለመሆኑ አንቺ ላልመሰለሽ ነገር ከመቸ ወዲህ ነው መጨነቅ የዠመርሽው? ዋናው ችግርሽ ሕይወትሽ ወደ አንድ ወገን.. ወደ ሥራ... ማዘመሙ... ሚዛን ማፋለሱ ነው። በዝኸ መኻል ነው ምንትዋብ የተጎዳችው። አየሽ የሰው ልዥ ጭንቅላት አንዱን የተፈጥሮ
ፍላጎቱን ችላ ብሎ ሌላውን ብቻ ይዞ መዝለቅ አይቻለውም። ይኸን
የጎደለበትን ማካካስ ሳይችል ሲቀር ችግር ውስጥ ይገባል። ጭንቅላት ተፈጥሮ ነውና ተፈጥሮ እንደምታደርገው ሚዛን መጠበቅ... ማካካስ አለበት ። አንቺም የጎደለውን እየሞላሽ ሚዛን እያስተካከልሽ ብትኸዲ
ሕይወትሽ የተቃና በሆነ።”
“እኔስ ግራ ገባኝ። እልም እያለምሁ ነው?”
“እያለምሽ ነው።”
“እያለምሁ ነው? እንግዲያማ ምን ፋይዳ አለው? እንደዝኸ ደስ
ሚል ነገር ነግረኸኝ እልም ነው ስትለኝ የሰጠኸኝን ተስፋ እየቀማኸኝ ማዶል?”
እየ ምንትዋብ! አስተዋይ ሴት ነሽ ግና ደሞ የዋህ ነሽ ። እልም
ፋይዳ የለውም ነው ምትይ? እልም እኮ አንዳንዴ ሚነግርሽ መልክት እንድትሞይ፣ ያዛባሽውን ሚዛን እንድታስተካክይ ላሳይሽ፣ ምልክት አለው። ሌላ ግዝየ ደሞ ያስጠነቅቅሻል። እኔ አሁን ያጎደልሽውን ልሰጥሽ ነው የመጣሁት።”
ያንን ካላት በኋላ፣ ያ ቀይ አበባ የመሰለ ነገር እየራቀና እየደበዘዘ
ሲሄድ፣ በምትኩ ኢያሱ - የአፄ በካፋ እህት ልጅ - ታያት። በነጭ
ተነፋነፍ ሱሪ ላይ ረጅም ነጭ ጥብቆ አድርጎ፣ ጥብቆው ላይ ነጠላ ለብሶ በላዩ ላይ ነጭ ካባ ደርቧል።
ኢያሱ... የወለተስራኤል ልዥ ... ኑሯል እንዴ ይኸን ሁሉ ሲለኝ
የነበረው? ስትል፣ ብንን አለች። ምን ያለ እልም ነው? ሲያቃዠኝ
ነው? አለችና አፏን ባንድ እጇ ይዛ ጣሪያ ጣሪያውን ተመለከተች።
ጉልህና ደስ የሚል ሕልም!
የሕልሟ ትርጉም ምን ሊሆን እንደሚችል መመርመር ጀመረች።
ቅዠት መሆን አለበት። የለም የለም ይኸ ቅዠት ማዶል... እልም
ነውና ... በገሀድ እያሳየኝ ውነት ነው ራሴን ጎድቻለሁ። ውነት ነው
ብቸኝነት እያጠቃኝ ነው። ዛዲያ ምን እያለኝ ነው? አግቢ? ባሌ
መተው ማግባት እንዴት ይቻለኛል? እንዴ ደሞ እረ ጉድ ነው
ኸሰው መኻል ኢያሱን ያሳየኝ ለምነው? አንድ ነገርማ አለ! እያለች ተገረመች።
የዛን ዕለት ጠዋት ኢያሱ ቤተመንግሥት እጅ ሊነሳ
ሲገባ ይኽ ሰው እንዲኽ መልከ መልካም ኑራል እንዴ? ያለችው ትዝ አላት።ምናልባትም እኮ እዝጊሃር ሊያመላክተኝ የፈለገው ነገር ይኖራል። ኸለዛ ኸሰው መኻል ስለምን እሱን በእልሜ ያመጣዋል? ነው አለወትሮየ
በእልሜ የመጣው? እያለች፣ አወጣች አወረደች። ተመልሳ ለመተኛት ሞከረች። እንቅልፍ አልወስድ ብሏት ስትገላበጥ ቆየች። ነገሩን የበለጠ
አሰበችበት፤ ከነከናት። እረ ስለምነው እንደዝኸ ለእልም መጨነቄ!ለዳግም ስለዝኸ ጉዳይ ማሰብ የለብኝም እያለች ስታሰላስል ነጋ።.....
✨ይቀጥላል✨
👍5
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
.....የምትለቀቀውማ እንደ ነገሩ ሁኔታ ዋስ ጠርተህ ነው» አለው መርማሪው ፖሊስ፣ ነገሩ የዕለት ግጭት በመሆኑ ብዙም ርቀት በማይሄድ ምርመራ እንደሚጠናቀቅ መርማሪው
ያስባል። የጠረጴዛ ደወል
አቃጨለና ረዳቱ ፖሊስ ሲቀርብለት ዓለሙን ወስዶ መብራቴ ባዩ የተባለ ሌላ
እስረኛ እንዲያቀርብለት አዘዘው።
ረዳቱም የተባለውን ፈፀመ፡
መብራቴ ባዩም በዕድሜው ብዙ አልገፋም ፣ ከሠላሳ ብዙ አያልፈውም፡፡ቀጠን ያለ ቀይ ዳማ ቢጤ ነው። መካከለኛ ቁመት አለው፡፡ ፀጉሩ አጠር፣ ከወደ አፉ
ሞጥሞጥ፣ ዓይኖቹ አነስ እነስ ያሉ ናቸው። እሱም በተመርማሪ ወንበር ላይ ተቀምጦ መርማሪውን በፍርሀት ይመለከተው ጀመር።
መርማሪው ፖሊስ ልክ በዓለሙ ላይ እንዳደረገው ሁሉ መብራቴን
መሠረታዊ መረጃዎችን እየጠየቀ ከመዘገበ በኋላ፡ «ከዓለሙ መርጋ ጋር ከአሁን በፊት ትተዋወቃላችሁ?» ሲል በቅድሚያ ጠየቀው።
«አይቸውም አላውቅ::»
«ምን አጣላችሁ ታዲያ?»
«እኔ ቀድሜ ገብቼ ባለሁበት ቤት መጥቶ ካልወጣህ ብሎ ሊያሳገድደኝ ሞከረ። አልወጣም ስለው በተቀመጥኩብት በጥፊ አቃጠለኝ ከዚያ በኋላ ነው
በደመነፍስ እጆቹን ይዤ ድረሱልኝ ብዬ የጮኩት።» አለው አይኖቹን እያቁለጨለጨ።
«በተጣላችሁበት ቤት ውስጥ ለምን ነበር ቀድመህ የገባኸው?»
«ቤቴ ነዋ!»
«ቤቴ ስትል? ሴትዮዋ ሚስትህ ናት?»
«ያው እንደ ሚሲቴ ናተ።»
«ለምን ያህል ጊዜ አብራችሁ ቆይታችኋል?»
«አረ ብዙ ነው።»
«እኮ በግምት?»
«ከአስራ አምስት ቀን በላይ አብረን አድረናል። ግን በተከታታይ
አደለም አልፎ አልፎ ነው፡፡ ከተዋወቅን ግን ቆይተናል፡፡»
«ወዳጅህ ስሟ ማን ይባላል?»
እየተገረመ ጠየቀው።
«ስሟ?»አለና መብራቴ ወደ ጣሪያ አንጋጠጠ፡፡ ግን ጠፋበት፡ ለማሰላሰል ሞከረና ሲያቅተው «ረሳሁት።» አለ የድንጋጤ ስሜት እየተነበበበት፡፡
«አሥራ አምስት ቀን ሙሉ የአቀፍካት ወዳጅህን» በማለት መርማሪው እየተገረመ ጠየቀው።
«በድንገት ስለሆነ የተገናኘነው ስሟ ይረሳኛል።»
መርማሪው ፖሊስ ጥርጣሬ ገባውና መብራቱን ትኩር ብሎ ተመለክተው።
መብራቴ የበለጠ የእፍረትና የድንጋጤ ስሜት ይነበብበት ጀመር።
«ዋሽተሃል አይደል?» አለው መርማሪው በትኩረት እየተመለከተው፡፡
«አጥፍቻለሁ ጌታዬ» አለ መብራቱ ሽቁጥቁጥ እያለ»
የመርማሪው ፖሊስ ልብ አሁንም እየተከረጢረ ሄደ ሆኖም ቃል
በያዘበት ወረቀት ላይ ከአስፈረመው በኋላ «የአንተንና የዓለሙን ጉዳይ በቀላሉ
ላለፈው አስቤ ነበር፡፡ ነገር ግን ተጠራጥሬአለሁ፡፡ የሁለታችሁንም ጉዳይ እንደገና
ኑነየው አልቀርም:: እለና ወደ እስር ቤት እንዲሄድ አሰናበተው፡፡
የመርማሪው ፖሊስ ጥርጣሬ ቀላል አልነበረም። ዓለሙን በሚጠይቅበት ወቅት ያያቸው ነነበሩ ሁኔታዎች እንደገና ትዝ አሉት። በስካር መንፈስ በአንዲት
ሴተኛ አዳሪ የተጣሉ መስለውት በእርግጥም ዋስ እያስጠራ በቀላሉ ሊሸኛቸው ነበር
አሳቡ:: አሁን ግን በጉዳዩ ላይ ጠለቅ ያለ ምርመራ ሊያደርግ ወሰነ። ለማንኛውም አለ በሆዱ
እስቲ ጋለሞታ የተባለችው ሴት ሌላ አጠራጣሪ ፍንጭ የምታወጣ
ከሆነ በቅድሚያ እሷን ላናጋግራት፡፡” አለና በረዳቱ ፖሲስ እንድትጠራ አደረገ።
ጋለሞታዋ ተጠርታ ወደ መርማሪው ፖሊስ ቢሮ በር ላይ ስትደርስ ሁለመናዋ በፍርሀት ይንቀጠቀጣል፡፡ እንባዋ ከዓይኗ ላይ እንደ በረዶ ይረግፋል።
መልኳ ደግሞ ይህ ቀረሽ የማትባል ወብ ናት። ዓይኖቿ እንደ ንጋት ኮከብ ያበራል። በዕድሜዋ ገና ወጣት ልጃገረድ ትመስላለች። “ጋለሞታ በሚለፈው የሴትነት መገለጫ አንዳች አመልካች ነገር አይታይባትም። ከንፈሮቿ እምቦጦች ይመስላሉ፡፡ የአፍንጫዋ አቀማመጥ ለቄንጥ የተሰራ ይመስላል። የቀይና ነጭ
ቡራቡራ ድሪያ ለብሳ በጡቶቿ ተገትሮ የአንጀቷን ድራሽ አጥፍቶታል።የመርማሪው ቢሮ በር ላይ ደርሳ ምን እንደምትባል ትዕዛዝ እየጠበቀች ሳለች
መርማሪው ፖሊስ ግን ይህንን ገፅታዋን ሲያይ ድንገት ተዘናግቶ ኖሮ ፐ! ይችስ ታደብድባለች አለ በሆዱ። ወዲያው ደግሞ «ምን ያስለቅስሻል?» ሲል ፈገግ ብሎ ጠየቃት ሁኔታዋ ሁሉ እያስገረመው። ግቢ ቁጭ በይ ማለቱን እንኳ እረሳው፡፡
«ፈርቼ» አለችው እንዳቀረቀረች::
«የሰራሽው ስራ አሳፈረሽ!»
«አረ እኔ ምንም አልሰራሁም!»
«እስቲ ግቢና ቁጭ በይ አላት» በእጁ አገጩን ያዝ አድርጎ አሁንም በትኩረት እየተመለከታት። ጋለሞታዋ ቁጭ አለችና አሁንም በፍርሃት ስሜት አቀርቅራ መሬት መሬት ታይ ጀመር።
«ምን አድርገሽ ነው የታሰርሽው?» ሲል ጠየቃት መርማሪው ፖላስ ቀስ እያለ ሊያግባባት ፈልጎ።
«ምንም» አለችና ለቅፅበት ያህል ቀና ብላ አየችው፡፡
«ዓለሙንና መብራቱን የት ነው የምታውቂያቸው?»
«እነማናቸው እነሱ?» አለች አሁንም፡፡ ለቅፅበት ያህል ቀና ብላ አይታው እንደገና እንጋቷን ደፋች::
«ጭራሽ አታወቂያቸውም?»
«አረ እኔ እንደዚህ የሚባሉ ሰዎች አላውቅም።»
«ሁለቱም ወዳጃችን ናት እያሉ እኮ ነው፡፡» አለና መርማሪው ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ ለምላሿ ጓጉቶ ይጠባበቃት ጀመር፡፡
"ኣ"አለችና እሁንዎ ቀና ብላ አየት አረገችው፡፡
«ከማናቸውም ጋር አብረሽ አድረሽ አታውቂም?»
«እኔ ከወንድ ጋር ተኝቼ አላውቅም፡፡»
«አንድም ቀን?»
«አንድ ቀን ብቻ ከምወደው ሰው ጋር አድሬ አውቃለሁ፡፡ ግን ከንፈሬን ስሞታል እንጂ ሌላ ምንም አላደረገኝም::»
«ማነው እሱ ደግሞ?» ሲል ጠየቃት መርማሬው።
«እሱ እዚህ አገር የለም፣ ኤርትራ እሚባል አገር ከሄደ ቆይቷል፡፡»
«ኦ!» አለ መርማሪው ፖሊስ አንዳች የማያውቀው ስሜት መላ ሰውነቱን ድንገት ወርር እያረገው፡፡ «ማን ይባላል?» ሲል እንደገና ጠየቃት::
«አስቻለው ፍስሀ»
«አስቻለው ፍስህ ?» ሲል ደግሞ ጠየቃት፡፡
«አዎ፡፡» አለችውና እሷም ድንግጥ ብላ ቀና ብላ ታየው ጀመር፡፡
«እንዴ!» አለና «መርማሪው እንደገና አትኩሮ ያያት ጀመር። ስሜቱ እያደር ተለዋወጠ፡፡ አንቺ ስምሽ ማን ይባላል?» ሲል ጠየቃት የምትሰጠው መልስ ቀድሞ እያስፈራው።
«ሔዋን ተስፋዬ::»
«ምን?» ሰምቶ እንዳልሰማ፡፡
«ሔዋን ተስፋዬ እባላለሁ።»
መርማሪው ፖሊስ ፍዝዝ ብሎ ቀረ፡፡ የያዘው እስኪርቢቶ ከእጁ ላይ ሾልኮ ሲወድቅ ፈጽሞ አልታወቀውም፡፡ ዲላ ከተማ እየኖረ ስለመሆኑ እንደ አዲስ
ታወቀው፡፡ በሀሳብ ጥቅልል ብሎ አስመራ ከተማ ገባ፡፡
መርማሪው ፖሊስ የሀምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ ይባላል። በሲዳሞ ክፍለ ሀገር በሀገረ ማሪያም ከተማ ተወልዶ ያደገ ነው። እዚያው በፖሊስነት ተቀጥሮ
እስከ ምክትል አሥር አለቅነት የደረሰና እሱም እንደ አስቻለው ፍሰሀ የዘመቻ ግዳጅ ተወስኖበት
ወደ ግንባር ዘምቶ በኤርትራ ምራባዊ የጦር ግንባሮች ለተከታታይ አምስት ዓመታት ሲዋጋ የቆየ ነው:: በጦር ግንባር የፈጸመው ጀብዱ የሀምሳ አለቅነት ማዕረግ ካገኘ በኋላ በቀጣይ የውጊያ ወቅት በደረሰበት ቁሰለት የተዋጊነት
ብቃቱ ቀንሶ ወደነበረበት የፖሊስ ሰራዊት አባልነቱ እንዲመለስ ተወስኖለት ወደ ሲዳም የተመለሰና ጊዜያዊ ምደባ ዲላ ውስጥ በመርማሪነት እየሰራ ያለ ፖሊስ ነው።
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
.....የምትለቀቀውማ እንደ ነገሩ ሁኔታ ዋስ ጠርተህ ነው» አለው መርማሪው ፖሊስ፣ ነገሩ የዕለት ግጭት በመሆኑ ብዙም ርቀት በማይሄድ ምርመራ እንደሚጠናቀቅ መርማሪው
ያስባል። የጠረጴዛ ደወል
አቃጨለና ረዳቱ ፖሊስ ሲቀርብለት ዓለሙን ወስዶ መብራቴ ባዩ የተባለ ሌላ
እስረኛ እንዲያቀርብለት አዘዘው።
ረዳቱም የተባለውን ፈፀመ፡
መብራቴ ባዩም በዕድሜው ብዙ አልገፋም ፣ ከሠላሳ ብዙ አያልፈውም፡፡ቀጠን ያለ ቀይ ዳማ ቢጤ ነው። መካከለኛ ቁመት አለው፡፡ ፀጉሩ አጠር፣ ከወደ አፉ
ሞጥሞጥ፣ ዓይኖቹ አነስ እነስ ያሉ ናቸው። እሱም በተመርማሪ ወንበር ላይ ተቀምጦ መርማሪውን በፍርሀት ይመለከተው ጀመር።
መርማሪው ፖሊስ ልክ በዓለሙ ላይ እንዳደረገው ሁሉ መብራቴን
መሠረታዊ መረጃዎችን እየጠየቀ ከመዘገበ በኋላ፡ «ከዓለሙ መርጋ ጋር ከአሁን በፊት ትተዋወቃላችሁ?» ሲል በቅድሚያ ጠየቀው።
«አይቸውም አላውቅ::»
«ምን አጣላችሁ ታዲያ?»
«እኔ ቀድሜ ገብቼ ባለሁበት ቤት መጥቶ ካልወጣህ ብሎ ሊያሳገድደኝ ሞከረ። አልወጣም ስለው በተቀመጥኩብት በጥፊ አቃጠለኝ ከዚያ በኋላ ነው
በደመነፍስ እጆቹን ይዤ ድረሱልኝ ብዬ የጮኩት።» አለው አይኖቹን እያቁለጨለጨ።
«በተጣላችሁበት ቤት ውስጥ ለምን ነበር ቀድመህ የገባኸው?»
«ቤቴ ነዋ!»
«ቤቴ ስትል? ሴትዮዋ ሚስትህ ናት?»
«ያው እንደ ሚሲቴ ናተ።»
«ለምን ያህል ጊዜ አብራችሁ ቆይታችኋል?»
«አረ ብዙ ነው።»
«እኮ በግምት?»
«ከአስራ አምስት ቀን በላይ አብረን አድረናል። ግን በተከታታይ
አደለም አልፎ አልፎ ነው፡፡ ከተዋወቅን ግን ቆይተናል፡፡»
«ወዳጅህ ስሟ ማን ይባላል?»
እየተገረመ ጠየቀው።
«ስሟ?»አለና መብራቴ ወደ ጣሪያ አንጋጠጠ፡፡ ግን ጠፋበት፡ ለማሰላሰል ሞከረና ሲያቅተው «ረሳሁት።» አለ የድንጋጤ ስሜት እየተነበበበት፡፡
«አሥራ አምስት ቀን ሙሉ የአቀፍካት ወዳጅህን» በማለት መርማሪው እየተገረመ ጠየቀው።
«በድንገት ስለሆነ የተገናኘነው ስሟ ይረሳኛል።»
መርማሪው ፖሊስ ጥርጣሬ ገባውና መብራቱን ትኩር ብሎ ተመለክተው።
መብራቴ የበለጠ የእፍረትና የድንጋጤ ስሜት ይነበብበት ጀመር።
«ዋሽተሃል አይደል?» አለው መርማሪው በትኩረት እየተመለከተው፡፡
«አጥፍቻለሁ ጌታዬ» አለ መብራቱ ሽቁጥቁጥ እያለ»
የመርማሪው ፖሊስ ልብ አሁንም እየተከረጢረ ሄደ ሆኖም ቃል
በያዘበት ወረቀት ላይ ከአስፈረመው በኋላ «የአንተንና የዓለሙን ጉዳይ በቀላሉ
ላለፈው አስቤ ነበር፡፡ ነገር ግን ተጠራጥሬአለሁ፡፡ የሁለታችሁንም ጉዳይ እንደገና
ኑነየው አልቀርም:: እለና ወደ እስር ቤት እንዲሄድ አሰናበተው፡፡
የመርማሪው ፖሊስ ጥርጣሬ ቀላል አልነበረም። ዓለሙን በሚጠይቅበት ወቅት ያያቸው ነነበሩ ሁኔታዎች እንደገና ትዝ አሉት። በስካር መንፈስ በአንዲት
ሴተኛ አዳሪ የተጣሉ መስለውት በእርግጥም ዋስ እያስጠራ በቀላሉ ሊሸኛቸው ነበር
አሳቡ:: አሁን ግን በጉዳዩ ላይ ጠለቅ ያለ ምርመራ ሊያደርግ ወሰነ። ለማንኛውም አለ በሆዱ
እስቲ ጋለሞታ የተባለችው ሴት ሌላ አጠራጣሪ ፍንጭ የምታወጣ
ከሆነ በቅድሚያ እሷን ላናጋግራት፡፡” አለና በረዳቱ ፖሲስ እንድትጠራ አደረገ።
ጋለሞታዋ ተጠርታ ወደ መርማሪው ፖሊስ ቢሮ በር ላይ ስትደርስ ሁለመናዋ በፍርሀት ይንቀጠቀጣል፡፡ እንባዋ ከዓይኗ ላይ እንደ በረዶ ይረግፋል።
መልኳ ደግሞ ይህ ቀረሽ የማትባል ወብ ናት። ዓይኖቿ እንደ ንጋት ኮከብ ያበራል። በዕድሜዋ ገና ወጣት ልጃገረድ ትመስላለች። “ጋለሞታ በሚለፈው የሴትነት መገለጫ አንዳች አመልካች ነገር አይታይባትም። ከንፈሮቿ እምቦጦች ይመስላሉ፡፡ የአፍንጫዋ አቀማመጥ ለቄንጥ የተሰራ ይመስላል። የቀይና ነጭ
ቡራቡራ ድሪያ ለብሳ በጡቶቿ ተገትሮ የአንጀቷን ድራሽ አጥፍቶታል።የመርማሪው ቢሮ በር ላይ ደርሳ ምን እንደምትባል ትዕዛዝ እየጠበቀች ሳለች
መርማሪው ፖሊስ ግን ይህንን ገፅታዋን ሲያይ ድንገት ተዘናግቶ ኖሮ ፐ! ይችስ ታደብድባለች አለ በሆዱ። ወዲያው ደግሞ «ምን ያስለቅስሻል?» ሲል ፈገግ ብሎ ጠየቃት ሁኔታዋ ሁሉ እያስገረመው። ግቢ ቁጭ በይ ማለቱን እንኳ እረሳው፡፡
«ፈርቼ» አለችው እንዳቀረቀረች::
«የሰራሽው ስራ አሳፈረሽ!»
«አረ እኔ ምንም አልሰራሁም!»
«እስቲ ግቢና ቁጭ በይ አላት» በእጁ አገጩን ያዝ አድርጎ አሁንም በትኩረት እየተመለከታት። ጋለሞታዋ ቁጭ አለችና አሁንም በፍርሃት ስሜት አቀርቅራ መሬት መሬት ታይ ጀመር።
«ምን አድርገሽ ነው የታሰርሽው?» ሲል ጠየቃት መርማሪው ፖላስ ቀስ እያለ ሊያግባባት ፈልጎ።
«ምንም» አለችና ለቅፅበት ያህል ቀና ብላ አየችው፡፡
«ዓለሙንና መብራቱን የት ነው የምታውቂያቸው?»
«እነማናቸው እነሱ?» አለች አሁንም፡፡ ለቅፅበት ያህል ቀና ብላ አይታው እንደገና እንጋቷን ደፋች::
«ጭራሽ አታወቂያቸውም?»
«አረ እኔ እንደዚህ የሚባሉ ሰዎች አላውቅም።»
«ሁለቱም ወዳጃችን ናት እያሉ እኮ ነው፡፡» አለና መርማሪው ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ ለምላሿ ጓጉቶ ይጠባበቃት ጀመር፡፡
"ኣ"አለችና እሁንዎ ቀና ብላ አየት አረገችው፡፡
«ከማናቸውም ጋር አብረሽ አድረሽ አታውቂም?»
«እኔ ከወንድ ጋር ተኝቼ አላውቅም፡፡»
«አንድም ቀን?»
«አንድ ቀን ብቻ ከምወደው ሰው ጋር አድሬ አውቃለሁ፡፡ ግን ከንፈሬን ስሞታል እንጂ ሌላ ምንም አላደረገኝም::»
«ማነው እሱ ደግሞ?» ሲል ጠየቃት መርማሬው።
«እሱ እዚህ አገር የለም፣ ኤርትራ እሚባል አገር ከሄደ ቆይቷል፡፡»
«ኦ!» አለ መርማሪው ፖሊስ አንዳች የማያውቀው ስሜት መላ ሰውነቱን ድንገት ወርር እያረገው፡፡ «ማን ይባላል?» ሲል እንደገና ጠየቃት::
«አስቻለው ፍስሀ»
«አስቻለው ፍስህ ?» ሲል ደግሞ ጠየቃት፡፡
«አዎ፡፡» አለችውና እሷም ድንግጥ ብላ ቀና ብላ ታየው ጀመር፡፡
«እንዴ!» አለና «መርማሪው እንደገና አትኩሮ ያያት ጀመር። ስሜቱ እያደር ተለዋወጠ፡፡ አንቺ ስምሽ ማን ይባላል?» ሲል ጠየቃት የምትሰጠው መልስ ቀድሞ እያስፈራው።
«ሔዋን ተስፋዬ::»
«ምን?» ሰምቶ እንዳልሰማ፡፡
«ሔዋን ተስፋዬ እባላለሁ።»
መርማሪው ፖሊስ ፍዝዝ ብሎ ቀረ፡፡ የያዘው እስኪርቢቶ ከእጁ ላይ ሾልኮ ሲወድቅ ፈጽሞ አልታወቀውም፡፡ ዲላ ከተማ እየኖረ ስለመሆኑ እንደ አዲስ
ታወቀው፡፡ በሀሳብ ጥቅልል ብሎ አስመራ ከተማ ገባ፡፡
መርማሪው ፖሊስ የሀምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ ይባላል። በሲዳሞ ክፍለ ሀገር በሀገረ ማሪያም ከተማ ተወልዶ ያደገ ነው። እዚያው በፖሊስነት ተቀጥሮ
እስከ ምክትል አሥር አለቅነት የደረሰና እሱም እንደ አስቻለው ፍሰሀ የዘመቻ ግዳጅ ተወስኖበት
ወደ ግንባር ዘምቶ በኤርትራ ምራባዊ የጦር ግንባሮች ለተከታታይ አምስት ዓመታት ሲዋጋ የቆየ ነው:: በጦር ግንባር የፈጸመው ጀብዱ የሀምሳ አለቅነት ማዕረግ ካገኘ በኋላ በቀጣይ የውጊያ ወቅት በደረሰበት ቁሰለት የተዋጊነት
ብቃቱ ቀንሶ ወደነበረበት የፖሊስ ሰራዊት አባልነቱ እንዲመለስ ተወስኖለት ወደ ሲዳም የተመለሰና ጊዜያዊ ምደባ ዲላ ውስጥ በመርማሪነት እየሰራ ያለ ፖሊስ ነው።
👍2
ከሁለት ዓመት በፊት ወደ ሲዳሞ ሲመለስ በተነሳበት ወቅት በአስመራ ከተማ ለጥቂት ቀናት ቆይቶ ነበር:: በእነዚያ ቀናት ውስጥ አንድ ቀደም ብሎ
ከሚያውቀው የአስመራ ነዋሪ ከሆነ ሰው ጋር 'ሳራዬ መናፈሻ ተብላ በምትታወቅ ቡና ቤት ቀጠሮ ይይዛል በቀጠሮ ቀን የሀምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ ከቀጠሮው ቦታ ቀድሞ ይደርሳል። ጓዳኛውን ለመጠበቅ እዚያው ቡና ቤት ውስጥ ብቻውን ይቀመጣል።
እሱ በተቀመጠበት ጠረጴዛ ማዶ ብቻውን የተቀመጠ ሰው ከዓይኑ ይገባል፡፡ያ ስው የአካል ጉዳተኛ ነው፡፡ የግራ እግሩ ተቆርጦ ሰው ሰራሽ እግር ተተክቶለታል። ቀኝ እጁም እንዲሁ ከአምባር መዋያው በታች ተቆርጦ በፕላስቲክ
ጣቶች የተተካ ነው፡፡ ከአጠገቡ ደግሞ ክራንች ግድግዳ ተደግፎ ቆሟል፡፡ የሰውዬው ግራ ፊት በእሳት የተለበለበ ይመስላል። ግራ ዓይነም የጠፋች ያህል ሆናለች፡፡ ግራ ጆሮው በጉዳት ምክንያት የተለጠፈች ስጋ እንጂ በእርግጥ ጆሮ አትመስልም፡፡
በዚሁ ላይ ውስጡም ሰላም ያለው አይመስልም፡፡ የሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ አትኩሮ ሲመለከተው ያ ሰው ያሚያስቦ የሚተክዝ ይመስለዋል። ፊቱ ቶሎ ቶሎ ይለዋወጣል፡፡ ብቻውን እንደሚያወራ ሁሉ ከንፈሮቹን ያነቃንቃል።
የሀምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ ያን ሰወዬ አከታትሎ እያየው ሳለ ያ
የቀጠረው ሰው ድንገት ይመጣል፡፡ ያ አካል ጉዳተኛ ከበሩ ፊትለፊት ተቀምጦ ነበርና የሀምሣ አለቃው ጓደኛ ቡና ቤቱ ውስጥ እንደገባ በቀጥታ ወደ ጉዳተኛው
ሰው በመሄድ ሰላም ይለዋል፡፡ ትንሽ ከተጠያየቁ በኋላ አዲስ መጪው ሰውየ ወደ ሀምሣ አለቃው ይመለሳል። እነሱም ሰላምታ ተለዋውጠው አብረው ቁጭ ይላሉ፡፡
መጠጥ አዝዘው መጠጣት ይጀምራሉ፡፡ በመሀል ሀምሣ አለቃው ስለዚያ አካል
ጉዳተኛ ሰው ጓደኛውን ይጠይቀዋል፡፡
«ያ ሰውየ ምን ሆኖ ነው? ከአካሉ መጎዳት በተጨማሪ ውስጡም ሰላም ያለው አይመስልም፡፡» ሲል ጓደኛውን ይጠይቀዋል፡፡
«እንደውም እኮ የአገርህ ሰው ነው፡፡»
የሲዳሞ?»
«አዎ፣ እንዳተው ለዘመቻ ተልኮ ነው የመጣው፡፡ በሙያው ሀኪም ነው። ጉዳት የደረሰበት ደግሞ በፈንጂ ነው፣ በአንድ ወቅት ያውም አስመራ ገብቶ ወር
እንኳ ሳይሞላው በተንቀሳቃሽ ክሊኒክ ወደ አንድ የጦር ግንባር ከሌሎች የሥራ ባልደረቦቹ ጋር ሲሄድ፡፡»
«ማን ይባላል?
«ነርስ አስቻለው ፍስህ ይባላል።»
የሃምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ ከንፈሩን መጠጠና «ላነጋግረው ይሆን?»
«በእናትህ እስቲ አነጋግረው፡፡»
የሆሃምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ አላመነታም ብድግ ብሉ ወደ አስቻለው ሄደ፡፡ እጁን ለሰላምታ እየዘረጋ የሃምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ እባላለሁ፡
«አስቻለው ፍስሃ » በማለት አስቻለውም ጨበጠው። የሃምሣ አለቃው ከአስቻለው አጠገብ ቁጭ እያለ
“ይቅርታ እስቻለው! የሀገሬ ልጅ መሆንህን ሰምቼ ላነጋግርህ ፈልጌ ነው፡፡» አለው
«የት አገር»
«የሲዳሞ ልጅ እያደለህም?»
አስቻለው ትንሽ ፈገግ ብሎ መሬት መሬት ካየ በኋላ፡ «በእርግጥ ሲዳማ ውስጥ እልወለድም:: ነገር ግን ወደዚህ የመጣሁት ለሥራ ከሄድኩበት ከዲላ ሆስፒታል ነው» ካለ በኋላ የሃምሳ አለቃውን ቀና ብሎ እያየ«አንተ ሲዳሞ የት
ላይ ነህ?» ሲል ጠየቀው::
«ውልደቴም ዕድገቴም በሀገረ ማሪያም ከተማ ነው፡፡»
«እእእ» አለና አስቻለው «በእርግጥም ዲላና ሀገረ ማርያም ቅርብ ለቅርብ
ናቸው::» እለው።
“ወዲህ ከመጣህ ቆየህ?» ሲል የሀ'ምሳ አለቃ ጠየቀው፡፡
«አዎ፡ ቆየት አልኩ፡፡»
«በግዳጅ እንደ መጣህ! ሰማሁ፡፡ አልጨረስክም?»
«አሁንም በግዳጅ ላይ ነኝ፡፡»
«መቼ ነው የምትጨርስ?»
«ዕድሜ ልክ ሳይሆንብኝ አይቀርም»
የሀምሣ አለቃው በአስቻለው መልስ ተጠራጠረና እየቀለደ ስለመስለው ፈገግ እያለ «እንዴ..ት?» ሲል ጠየቀው፡ ወዲያው ደግሞ አንድ አስተናጋጅ ጠራና ቀድሞ ከነበረበት ጠረጴዛ ላይ የጀመረውን የቢራ ጠርሙስ እንዲያመጣለት አዘዘው::
«ምነው ጓደኛህን ትተህ?» አለው ከስቻለው ቀና ብሎ እያየው፡፡»
«ከሀገሬ ልጅ ጋር መጫወት ፈልኩ»:: አለና የሀምሳ አለቃ እስቲ ምናምኘሰ ውሰድ። ከነገ ወዲያ ወደ ሀገሬ ልመለስ ነውና የወጪ ልበልህ፡፡» ሲል ጋበዘው፡፡
«ይኸው ጠጣሁእኮ»! አለ አስቻለው ቀደም ሲል አጠገቡ የነበረ የለስላሳ ጠርሙስ እያሳየው፡፡
«ሌላ ነገር፡»
«ምንም እልጠጣም»
«ቢራ ጠጣ፡፡»
«አልኮል ጭራሽ አልጠጣም:: ሻይ ቡናም ቀደም ብዬ ጠጥቻለሁ አመሰግናለሁ::» አለ አስቻለው በማከታተል፡፡
የሀምሣ አለቃው ወደ ጨዋታው ተመለሰ። ወደ ሲዳሞ የመመለስ ዕቅድ የለህም?» ሲል ጠየቀው፡፡
«የለኝም»
«ለምን?»
«በቃ ስላልፈለኩ ብቻ ነው»
«እስከ መጨረሻው?»
በዚህ ጊዜ እስቻለው ፊቱን ወደ ጣሪያ መለስና ዓይኑን በኮርኒስ ላይ ሰካ ፍዝዝ ትክዝ አለ፡፡ ደስ የማይል ስሜት በፊቱ ላይ መነበብ ጀመረ፡፡ በዚያው ልክ የሃምሣ አለቃውም በአስቻለው ሆድ ውስጥ የተቀበረ አንድ ነገር እንዳለ ገባውና፡
«ችግር አለ እንዴ የኔ ወንድም?» ሲል ትኩር ብሎ እያየ ጠየቀው።
አስቻለው ድንገት ወደ ቀልቡ እንደመመለስ አለና «አይ አይ ችግር የለም። ወደ ሲዳሞ በስተርጅና ዕድሜዬ ብቅ ማለት አስባለሁ፡፡» ካለ በኋላ ወደ ሃምሳ አለቃው ቀና በማለት ፈገግ እያለ
«ግን ደግሞ ከሀገሬ በፊትእኔ ቀድሜ ካረጀሁ » አለው
«አልገባኝም::»
«የሀገር እርጅና፡፡»
አስቻለው ወደ መሬት አቀረቀረና ራሱን ወዘወዘ አውቆም ይሁን ሳያውቅ ከንፈሩን ነከሰ።....
💫ይቀጥላል💫
ከሚያውቀው የአስመራ ነዋሪ ከሆነ ሰው ጋር 'ሳራዬ መናፈሻ ተብላ በምትታወቅ ቡና ቤት ቀጠሮ ይይዛል በቀጠሮ ቀን የሀምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ ከቀጠሮው ቦታ ቀድሞ ይደርሳል። ጓዳኛውን ለመጠበቅ እዚያው ቡና ቤት ውስጥ ብቻውን ይቀመጣል።
እሱ በተቀመጠበት ጠረጴዛ ማዶ ብቻውን የተቀመጠ ሰው ከዓይኑ ይገባል፡፡ያ ስው የአካል ጉዳተኛ ነው፡፡ የግራ እግሩ ተቆርጦ ሰው ሰራሽ እግር ተተክቶለታል። ቀኝ እጁም እንዲሁ ከአምባር መዋያው በታች ተቆርጦ በፕላስቲክ
ጣቶች የተተካ ነው፡፡ ከአጠገቡ ደግሞ ክራንች ግድግዳ ተደግፎ ቆሟል፡፡ የሰውዬው ግራ ፊት በእሳት የተለበለበ ይመስላል። ግራ ዓይነም የጠፋች ያህል ሆናለች፡፡ ግራ ጆሮው በጉዳት ምክንያት የተለጠፈች ስጋ እንጂ በእርግጥ ጆሮ አትመስልም፡፡
በዚሁ ላይ ውስጡም ሰላም ያለው አይመስልም፡፡ የሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ አትኩሮ ሲመለከተው ያ ሰው ያሚያስቦ የሚተክዝ ይመስለዋል። ፊቱ ቶሎ ቶሎ ይለዋወጣል፡፡ ብቻውን እንደሚያወራ ሁሉ ከንፈሮቹን ያነቃንቃል።
የሀምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ ያን ሰወዬ አከታትሎ እያየው ሳለ ያ
የቀጠረው ሰው ድንገት ይመጣል፡፡ ያ አካል ጉዳተኛ ከበሩ ፊትለፊት ተቀምጦ ነበርና የሀምሣ አለቃው ጓደኛ ቡና ቤቱ ውስጥ እንደገባ በቀጥታ ወደ ጉዳተኛው
ሰው በመሄድ ሰላም ይለዋል፡፡ ትንሽ ከተጠያየቁ በኋላ አዲስ መጪው ሰውየ ወደ ሀምሣ አለቃው ይመለሳል። እነሱም ሰላምታ ተለዋውጠው አብረው ቁጭ ይላሉ፡፡
መጠጥ አዝዘው መጠጣት ይጀምራሉ፡፡ በመሀል ሀምሣ አለቃው ስለዚያ አካል
ጉዳተኛ ሰው ጓደኛውን ይጠይቀዋል፡፡
«ያ ሰውየ ምን ሆኖ ነው? ከአካሉ መጎዳት በተጨማሪ ውስጡም ሰላም ያለው አይመስልም፡፡» ሲል ጓደኛውን ይጠይቀዋል፡፡
«እንደውም እኮ የአገርህ ሰው ነው፡፡»
የሲዳሞ?»
«አዎ፣ እንዳተው ለዘመቻ ተልኮ ነው የመጣው፡፡ በሙያው ሀኪም ነው። ጉዳት የደረሰበት ደግሞ በፈንጂ ነው፣ በአንድ ወቅት ያውም አስመራ ገብቶ ወር
እንኳ ሳይሞላው በተንቀሳቃሽ ክሊኒክ ወደ አንድ የጦር ግንባር ከሌሎች የሥራ ባልደረቦቹ ጋር ሲሄድ፡፡»
«ማን ይባላል?
«ነርስ አስቻለው ፍስህ ይባላል።»
የሃምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ ከንፈሩን መጠጠና «ላነጋግረው ይሆን?»
«በእናትህ እስቲ አነጋግረው፡፡»
የሆሃምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ አላመነታም ብድግ ብሉ ወደ አስቻለው ሄደ፡፡ እጁን ለሰላምታ እየዘረጋ የሃምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ እባላለሁ፡
«አስቻለው ፍስሃ » በማለት አስቻለውም ጨበጠው። የሃምሣ አለቃው ከአስቻለው አጠገብ ቁጭ እያለ
“ይቅርታ እስቻለው! የሀገሬ ልጅ መሆንህን ሰምቼ ላነጋግርህ ፈልጌ ነው፡፡» አለው
«የት አገር»
«የሲዳሞ ልጅ እያደለህም?»
አስቻለው ትንሽ ፈገግ ብሎ መሬት መሬት ካየ በኋላ፡ «በእርግጥ ሲዳማ ውስጥ እልወለድም:: ነገር ግን ወደዚህ የመጣሁት ለሥራ ከሄድኩበት ከዲላ ሆስፒታል ነው» ካለ በኋላ የሃምሳ አለቃውን ቀና ብሎ እያየ«አንተ ሲዳሞ የት
ላይ ነህ?» ሲል ጠየቀው::
«ውልደቴም ዕድገቴም በሀገረ ማሪያም ከተማ ነው፡፡»
«እእእ» አለና አስቻለው «በእርግጥም ዲላና ሀገረ ማርያም ቅርብ ለቅርብ
ናቸው::» እለው።
“ወዲህ ከመጣህ ቆየህ?» ሲል የሀ'ምሳ አለቃ ጠየቀው፡፡
«አዎ፡ ቆየት አልኩ፡፡»
«በግዳጅ እንደ መጣህ! ሰማሁ፡፡ አልጨረስክም?»
«አሁንም በግዳጅ ላይ ነኝ፡፡»
«መቼ ነው የምትጨርስ?»
«ዕድሜ ልክ ሳይሆንብኝ አይቀርም»
የሀምሣ አለቃው በአስቻለው መልስ ተጠራጠረና እየቀለደ ስለመስለው ፈገግ እያለ «እንዴ..ት?» ሲል ጠየቀው፡ ወዲያው ደግሞ አንድ አስተናጋጅ ጠራና ቀድሞ ከነበረበት ጠረጴዛ ላይ የጀመረውን የቢራ ጠርሙስ እንዲያመጣለት አዘዘው::
«ምነው ጓደኛህን ትተህ?» አለው ከስቻለው ቀና ብሎ እያየው፡፡»
«ከሀገሬ ልጅ ጋር መጫወት ፈልኩ»:: አለና የሀምሳ አለቃ እስቲ ምናምኘሰ ውሰድ። ከነገ ወዲያ ወደ ሀገሬ ልመለስ ነውና የወጪ ልበልህ፡፡» ሲል ጋበዘው፡፡
«ይኸው ጠጣሁእኮ»! አለ አስቻለው ቀደም ሲል አጠገቡ የነበረ የለስላሳ ጠርሙስ እያሳየው፡፡
«ሌላ ነገር፡»
«ምንም እልጠጣም»
«ቢራ ጠጣ፡፡»
«አልኮል ጭራሽ አልጠጣም:: ሻይ ቡናም ቀደም ብዬ ጠጥቻለሁ አመሰግናለሁ::» አለ አስቻለው በማከታተል፡፡
የሀምሣ አለቃው ወደ ጨዋታው ተመለሰ። ወደ ሲዳሞ የመመለስ ዕቅድ የለህም?» ሲል ጠየቀው፡፡
«የለኝም»
«ለምን?»
«በቃ ስላልፈለኩ ብቻ ነው»
«እስከ መጨረሻው?»
በዚህ ጊዜ እስቻለው ፊቱን ወደ ጣሪያ መለስና ዓይኑን በኮርኒስ ላይ ሰካ ፍዝዝ ትክዝ አለ፡፡ ደስ የማይል ስሜት በፊቱ ላይ መነበብ ጀመረ፡፡ በዚያው ልክ የሃምሣ አለቃውም በአስቻለው ሆድ ውስጥ የተቀበረ አንድ ነገር እንዳለ ገባውና፡
«ችግር አለ እንዴ የኔ ወንድም?» ሲል ትኩር ብሎ እያየ ጠየቀው።
አስቻለው ድንገት ወደ ቀልቡ እንደመመለስ አለና «አይ አይ ችግር የለም። ወደ ሲዳሞ በስተርጅና ዕድሜዬ ብቅ ማለት አስባለሁ፡፡» ካለ በኋላ ወደ ሃምሳ አለቃው ቀና በማለት ፈገግ እያለ
«ግን ደግሞ ከሀገሬ በፊትእኔ ቀድሜ ካረጀሁ » አለው
«አልገባኝም::»
«የሀገር እርጅና፡፡»
አስቻለው ወደ መሬት አቀረቀረና ራሱን ወዘወዘ አውቆም ይሁን ሳያውቅ ከንፈሩን ነከሰ።....
💫ይቀጥላል💫
👍4😢1
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...የዛን ዕለት ጠዋት ኢያሱ ቤተመንግሥት እጅ ሊነሳ
ሲገባ ይኽ ሰው እንዲኽ መልከ መልካም ኑራል እንዴ? ያለችው ትዝ አላት።ምናልባትም እኮ እዝጊሃር ሊያመላክተኝ የፈለገው ነገር ይኖራል። ኸለዛ ኸሰው መኻል ስለምን እሱን በእልሜ ያመጣዋል? ነው አለወትሮየ
በእልሜ የመጣው? እያለች፣ አወጣች አወረደች። ተመልሳ ለመተኛት ሞከረች። እንቅልፍ አልወስድ ብሏት ስትገላበጥ ቆየች። ነገሩን የበለጠ
አሰበችበት፤ ከነከናት። እረ ስለምነው እንደዝኸ ለእልም መጨነቄ!ለዳግም ስለዝኸ ጉዳይ ማሰብ የለብኝም እያለች ስታሰላስል ነጋ።
ከዚያን ቀን ጀምሮ ኢያሱን ከሐሳቧ ማውጣት አቃታት። ጭንቅላቷ
ከእሱ ሌላ ማሰብ ተሳነው። ይኸ ሰው እኮ የጃንሆይ እት ልዥ ነው።
እንዴት ሁኖ ነው ኸሱ ጋር ሰውስ ምን ይላል? ይቅርብኝ ይኸ ነገር፡
አግባብ ማዶል። የጃንሆይ አጥንት ይወቅሰኛል። ለስሜም ለልዥም
ክብር ተገቢ ማዶል። ልዝም ቢሆን ሲያድግ ያባቴ ክብር ተነካ
ብሎ መቀየሙ አይቀርም፡፡ አምላኬ ምነው እንደዝኸ ያለ መፈታተኛ ሰጠኸኝ? እያለች አምላኳን ሞገተች።
የራሷን ፍላጎትና የሰዉን አመለካከት ስታወዳድር፣ ስታመዛዝን፣ስትጨነቅ፣ ልቧ ሲማስን ወራት አለፉ። ኢያሱ፣ መጥቶ እንደወትሯቸው
እንዳይጫወቱ ምክንያት እየሰጠች ከቤተመንግሥት እንዲርቅ አደረገችው። ውስጧ ለሚንቀለቀለውም ስሜት ልጓም ልታበጅለት ፈለገች። ኅሊናዋ አንዴ ሲከሳት፣ ሌላ ጊዜ ሲፈርድባት፣ አንቺ የቁስቋሟ፡
ይኸን ነገር ኸልቤ አውጭልኝ እያለች ማርያምን ተማፀነች።
ልቧ ግን ወደ እሱ አዘነበለ። የፍቅርን ዕርከን እያዘገመ ወጣ። እንደ እምቡጥ ጽጌሬዳ ራሱ የፈነዳና የአበበ ንፁህ ፍቅር በውስጡ ሰረፀ። በሠራ አካላቷ ተበተነ፣ ዐዲስ ሕይወት በመላ ሰውነቷ ውስጥ አንሰራራ፣
የጎደለው ልቧ ሞላ።
ኢያሱም ቢሆን አጎቱ ከሞቱ በኋላ፣ ቤተመንግሥት አዘውትሮ
መምጣቱ አለነገሩ እንዳልሆነ ገባት። የእሱም ልብ መዋለሉን ተረዳች።ከሰው መሀል ዝምታው ሲያነጋግራት፣ ዐይኖቿ የፍቅር ግብር ሲልኩ፣ገፅታው ጥያቄዎቿን ሲመልስላት ልቧ ከልቡ እንደተጣመረ አወቀች።
ኅሊናዋ መሞገቱን ተወ። ጭራሽ ገፋፋት፤ አሻፈረኝ፣ ባህልና ሥርዐት አያግደኝ በይ አላት።
የወደደ የተሸሽገን አያጣውም እንዲሉ፣ ኢያሱን ለብቻው እልፍኟ
ማስጠራት ጀመረች። ሲመጣ፣ እንደ ማንኛውም ሰው ማውራትና
መጫወት ትፈልጋለች። ዘውዷን አውርዳ፣ ካባዋን ወርውራ፣ እቴጌ
ሳትሆን ሰው ሆና ትጠብቀዋለች።
መስተዋት ፊት ስትቆም፣ ዕድሜ አካሏ ላይ ያመጣውን ለውጥ
ለመፈተሽ ወደ መስተዋቱ ስትጠጋ፣ ያቺ ቋራን ስትለቅ ዐዲስ የፈነዳ አበባ የመሰለችው ወጣት ዛሬ ዕድሜ ሰውነቷን ሞልቶ፣ አካሏንና አእምሮዋን አዳብሮ በውበት ላይ ውበት አክሎላት ገና የደረሰ ፍሬ መምሰሏ አልታወቅ ይላታል። ግንባሯን ፈታ፣ ጨምደድ አድርጋ፣ ወደ መስተዋቱ ጠጋ፣ ራቅ ስትል ያሉትም የሌሉትም መስመሮች ይታይዋታል። እህል በልቶ የሚያውቅ የማይመስለውን ወገቧን ወደ ጎን፣ ወደ ፊትና ወደ ኋላ እያለች ትመለከትና ያች የቋራዋ ጉብል ኣልመስል ትላታለች፡፡
ያን ሰዐት ግዝየ ሌባ ነው ትላለች።
ኢያሱን ለብቻው ማግኘት ስትጀምር፣ ወሬው ከቤተመንግሥት ባለሟሎች ሹክሹክታ አልፎ መሣፍንቱ፣ መኳንንቱ፣ ካህናቱ፣ ሊቃውንቱና
ወይዛዝርቱ መሃል፣ ብሎም ሕዝቡጋ ደረሰ፤ “እቴጌ ኸባላቸው እት ልዥ ጋር ወዳጅነት ያዙ” እየተባለ ተናፈሰ።
ምንትዋብ ግን ወሬውን ከቁብም አልቆጠረችው።
ጭራሹን ከኢያሱ ጋር በድብቅ ተጋቡ። ጐንደሬዎች “ምልምል
የሚል ቅጽል ስም... የተመረጠው ለማለት... አወጡለት። ምንትዋብ
ምልምል እንዳይሉት ግራዝማች አለችው። ግራዝማች ኢያሱ የሰጣትን ዐዲስ የተገኘ ነፃነት ወደደችው። በልጅነቷ ቤተመንግሥት ገብታ ሕይወቷ በወግ ታጥሮ ቆይቶ አሁን እንደ ተራ ሰው መወደድ እናት መወደድ መቻሏ ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ሰጠው።
አንድ ቀን ግን ይህንን ትርጉም የሚገዳደር፣ ነፃነቷን የሚያውክ ነገር ተፈጠረ። ጠዋት ላይ እልፍኟ ተቀምጣ በሐሳብ ዥው ብላለች፤ ከፊሉን ጊዜ ስለ ኢያሱ፣ ከፊሉን ጊዜ ደግሞ ስለ ግብር አዳራሽ ግንባታ ታስባለች።
ዋና የእልፍኝ አስከልካዩ አርከኤድስ ለጥ ብሎ እጅ ነሳና፣ “አንድ መነኩሴ ኸነማይ መልክት ይዤ መጥቻለሁ ብለው በር ላይ ናቸው።
የውጭ በር ላይ አላስገባ ብለዋቸው መመላለሳቸውን ብሰማ፣ ግቢ እንዲገቡ አርጌ አነጋገርኳቸው። 'ስመላለስ ከረምሁ፣ ብዙም ተጉላላሁ።
አገሬ መመለሻ ግዝየ በመጉላላት አለፈ። ለእቴጌ በእጅ ስጥ ተብየ
ይዤ የመጣሁትን መልክት እንዴት አድርጌ ይዤ መለሳለሁ እያልሁ
ኸዝሁ ከረምሁ እያሉ ቢጨነቁ ይጠብቁ ብያቸው መጣሁ” አላት።
“ኸነማይ?” አለች፣ ምንትዋብ ተገርማ። ከነማይ ማን መልዕክት
ሊልክላት እንዲሚችል መገመት አቅቷት።
“አዎ... ዘመድ ልኮኝ ነው አሉ። የተጠቀለለ ነገር ይዘዋል። “ለእቴጌ በጃቸው በቀር ለሌላ እንዳትሰጥ ብለው አስምለውኝ ነው ያመጣሁት ይላሉ።”
የማናቸው መነኩሴ? እያለች ትንሽ ካሰበች በኋላ፣ “ይግቡ!" አለችው።
አዛዥ አርከሌድስ እጅ ነስቶ ወጣ። ጥቂት ቆይቶ በእሱ መሪነት
ቆብ የደፉ፣ ረጅምና ሰፊ ቀሚስ ያጠለቁ፣ ሽማግሌ ሰው ገብተው
መሬት ሊስሙ ሲያጎነብሱ፣ “ግድ የለም አባቴ ይቀመጡ” አለቻቸው፣ ምንትዋብ።
ፈንጠር ብለው ወንበር ላይ ተቀመጡ።
“አባቴ ኸየት መጡ? ደሞስ ማን ልኮዎት ነው የመጡ?” አለቻቸው። መነኩሴው ከተቀመጡበት ተነሥተው ለጥ ብለው እጅ ነሱ። “እቴጌ ዝናዎን ስሰማ ቆይቸ ዛሬ እርሶን ለማየት ያበቃችኝ ኪዳነ ምረት
ምስጋና ይግባት። እቴጌ ኸነማይ ነው የመጣሁ። ደፈጫ ኪዳነ ምረት ስለት ነበረኝና እሱን ላደርስ መኸዴ ነው ብየ ስነሳ አንድ ኸኛ ዘንድ ሚመላለሱ ሰው፣ '
እኼን ለእቴጌ እንደምንም ብለው አድርሱልኝ። ዐደራ በእጅ ይስጡልኝ። ዘመድ ነኝ ቢሉኝ አመንኳቸው።”
“ሰውየው ማን ይባለሉ?”
“እቴጌ ዕቃውን ሲያዩ ማን እንደሆንሁ ያቃሉ ብለውኛል” ብለው ጥቅሉን አሳዩ።
ምንትዋብ፣ አርከሌድስን፣ “ተቀበልና ፍታው” አለችው።
“እቴጌ ኸርሶ በቀር ለሌላ አትስጥ ተብያለሁ” አሉ፣ መነኩሴው፣
ብድግ ብለው።
“ይቀመጡ... ይስጡትና እኔ ፈታዋለሁ።”
ጥቅሉን ለአርከሌድስ ሲሰጡት ተቀብላ ስትፈታው ዐራት ማዕዘን
እንጨት ላይ የተሣለ የራሷ ምስል ነው። ነጠላ ተከናንባ ወፍታ ጊዮርጊስ ደጀሰላም ላይ ነው። መብረቅ የመታት ያህል ክው ብላ ቀረች።
መነኩሴው የፊቷን መለዋወጥ አይተው ደነገጡ። ከተቀመጡበት
ተነሱ። “እቴጌ... ክፉ ነገር ኑሯል?” ሲሉ ጠየቋት።
የለ፣ ደግ ነው። ብቻ ያልጠበቅሁት ነገር ሁኖብኝ ነው። የላክሁ
ሰውየ ስማቸው ማነው ነበር ያሉኝ?”.
ስማቸውን ስንኳ አላወቅሁም። እኔ ብዙ ግዝየን ኸሰው ስለማልገናኝ
ስለሰዎች እምብዛም አላውቅም። 'እነማይ ለጉዳይ መጠቼ፣ ጐንደር“
ይኸዳሉ ሲሉ ብሰማ ተላኩኝ ብየ ነው። ለእቴጌም ዘመድ ነኝ። የእቴጌ አያቶች እኮ ትውልዳቸው ኸዝሁ ኸኛው ዘንድ ነው ቢሉኝ ምን ከፋኝ ብየ ይዤ መጣሁ።”
“ወደ እነማይ በቅርቡ ይመለሳሉ?”
“ለርሶ መልክቴን ካደረስሁ እንግዲህ ነገ እነሳለሁ።”
“እንግዲያማ ደሕና ግቡ። ለላኩዎም ሰው ባክዎን ወደ ጐንደር ብቅ ይበሉ። እንደርሶ ያለ ሠዓሊ ፈልጋለሁ ይበሉልኝ” አለቻቸው።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...የዛን ዕለት ጠዋት ኢያሱ ቤተመንግሥት እጅ ሊነሳ
ሲገባ ይኽ ሰው እንዲኽ መልከ መልካም ኑራል እንዴ? ያለችው ትዝ አላት።ምናልባትም እኮ እዝጊሃር ሊያመላክተኝ የፈለገው ነገር ይኖራል። ኸለዛ ኸሰው መኻል ስለምን እሱን በእልሜ ያመጣዋል? ነው አለወትሮየ
በእልሜ የመጣው? እያለች፣ አወጣች አወረደች። ተመልሳ ለመተኛት ሞከረች። እንቅልፍ አልወስድ ብሏት ስትገላበጥ ቆየች። ነገሩን የበለጠ
አሰበችበት፤ ከነከናት። እረ ስለምነው እንደዝኸ ለእልም መጨነቄ!ለዳግም ስለዝኸ ጉዳይ ማሰብ የለብኝም እያለች ስታሰላስል ነጋ።
ከዚያን ቀን ጀምሮ ኢያሱን ከሐሳቧ ማውጣት አቃታት። ጭንቅላቷ
ከእሱ ሌላ ማሰብ ተሳነው። ይኸ ሰው እኮ የጃንሆይ እት ልዥ ነው።
እንዴት ሁኖ ነው ኸሱ ጋር ሰውስ ምን ይላል? ይቅርብኝ ይኸ ነገር፡
አግባብ ማዶል። የጃንሆይ አጥንት ይወቅሰኛል። ለስሜም ለልዥም
ክብር ተገቢ ማዶል። ልዝም ቢሆን ሲያድግ ያባቴ ክብር ተነካ
ብሎ መቀየሙ አይቀርም፡፡ አምላኬ ምነው እንደዝኸ ያለ መፈታተኛ ሰጠኸኝ? እያለች አምላኳን ሞገተች።
የራሷን ፍላጎትና የሰዉን አመለካከት ስታወዳድር፣ ስታመዛዝን፣ስትጨነቅ፣ ልቧ ሲማስን ወራት አለፉ። ኢያሱ፣ መጥቶ እንደወትሯቸው
እንዳይጫወቱ ምክንያት እየሰጠች ከቤተመንግሥት እንዲርቅ አደረገችው። ውስጧ ለሚንቀለቀለውም ስሜት ልጓም ልታበጅለት ፈለገች። ኅሊናዋ አንዴ ሲከሳት፣ ሌላ ጊዜ ሲፈርድባት፣ አንቺ የቁስቋሟ፡
ይኸን ነገር ኸልቤ አውጭልኝ እያለች ማርያምን ተማፀነች።
ልቧ ግን ወደ እሱ አዘነበለ። የፍቅርን ዕርከን እያዘገመ ወጣ። እንደ እምቡጥ ጽጌሬዳ ራሱ የፈነዳና የአበበ ንፁህ ፍቅር በውስጡ ሰረፀ። በሠራ አካላቷ ተበተነ፣ ዐዲስ ሕይወት በመላ ሰውነቷ ውስጥ አንሰራራ፣
የጎደለው ልቧ ሞላ።
ኢያሱም ቢሆን አጎቱ ከሞቱ በኋላ፣ ቤተመንግሥት አዘውትሮ
መምጣቱ አለነገሩ እንዳልሆነ ገባት። የእሱም ልብ መዋለሉን ተረዳች።ከሰው መሀል ዝምታው ሲያነጋግራት፣ ዐይኖቿ የፍቅር ግብር ሲልኩ፣ገፅታው ጥያቄዎቿን ሲመልስላት ልቧ ከልቡ እንደተጣመረ አወቀች።
ኅሊናዋ መሞገቱን ተወ። ጭራሽ ገፋፋት፤ አሻፈረኝ፣ ባህልና ሥርዐት አያግደኝ በይ አላት።
የወደደ የተሸሽገን አያጣውም እንዲሉ፣ ኢያሱን ለብቻው እልፍኟ
ማስጠራት ጀመረች። ሲመጣ፣ እንደ ማንኛውም ሰው ማውራትና
መጫወት ትፈልጋለች። ዘውዷን አውርዳ፣ ካባዋን ወርውራ፣ እቴጌ
ሳትሆን ሰው ሆና ትጠብቀዋለች።
መስተዋት ፊት ስትቆም፣ ዕድሜ አካሏ ላይ ያመጣውን ለውጥ
ለመፈተሽ ወደ መስተዋቱ ስትጠጋ፣ ያቺ ቋራን ስትለቅ ዐዲስ የፈነዳ አበባ የመሰለችው ወጣት ዛሬ ዕድሜ ሰውነቷን ሞልቶ፣ አካሏንና አእምሮዋን አዳብሮ በውበት ላይ ውበት አክሎላት ገና የደረሰ ፍሬ መምሰሏ አልታወቅ ይላታል። ግንባሯን ፈታ፣ ጨምደድ አድርጋ፣ ወደ መስተዋቱ ጠጋ፣ ራቅ ስትል ያሉትም የሌሉትም መስመሮች ይታይዋታል። እህል በልቶ የሚያውቅ የማይመስለውን ወገቧን ወደ ጎን፣ ወደ ፊትና ወደ ኋላ እያለች ትመለከትና ያች የቋራዋ ጉብል ኣልመስል ትላታለች፡፡
ያን ሰዐት ግዝየ ሌባ ነው ትላለች።
ኢያሱን ለብቻው ማግኘት ስትጀምር፣ ወሬው ከቤተመንግሥት ባለሟሎች ሹክሹክታ አልፎ መሣፍንቱ፣ መኳንንቱ፣ ካህናቱ፣ ሊቃውንቱና
ወይዛዝርቱ መሃል፣ ብሎም ሕዝቡጋ ደረሰ፤ “እቴጌ ኸባላቸው እት ልዥ ጋር ወዳጅነት ያዙ” እየተባለ ተናፈሰ።
ምንትዋብ ግን ወሬውን ከቁብም አልቆጠረችው።
ጭራሹን ከኢያሱ ጋር በድብቅ ተጋቡ። ጐንደሬዎች “ምልምል
የሚል ቅጽል ስም... የተመረጠው ለማለት... አወጡለት። ምንትዋብ
ምልምል እንዳይሉት ግራዝማች አለችው። ግራዝማች ኢያሱ የሰጣትን ዐዲስ የተገኘ ነፃነት ወደደችው። በልጅነቷ ቤተመንግሥት ገብታ ሕይወቷ በወግ ታጥሮ ቆይቶ አሁን እንደ ተራ ሰው መወደድ እናት መወደድ መቻሏ ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ሰጠው።
አንድ ቀን ግን ይህንን ትርጉም የሚገዳደር፣ ነፃነቷን የሚያውክ ነገር ተፈጠረ። ጠዋት ላይ እልፍኟ ተቀምጣ በሐሳብ ዥው ብላለች፤ ከፊሉን ጊዜ ስለ ኢያሱ፣ ከፊሉን ጊዜ ደግሞ ስለ ግብር አዳራሽ ግንባታ ታስባለች።
ዋና የእልፍኝ አስከልካዩ አርከኤድስ ለጥ ብሎ እጅ ነሳና፣ “አንድ መነኩሴ ኸነማይ መልክት ይዤ መጥቻለሁ ብለው በር ላይ ናቸው።
የውጭ በር ላይ አላስገባ ብለዋቸው መመላለሳቸውን ብሰማ፣ ግቢ እንዲገቡ አርጌ አነጋገርኳቸው። 'ስመላለስ ከረምሁ፣ ብዙም ተጉላላሁ።
አገሬ መመለሻ ግዝየ በመጉላላት አለፈ። ለእቴጌ በእጅ ስጥ ተብየ
ይዤ የመጣሁትን መልክት እንዴት አድርጌ ይዤ መለሳለሁ እያልሁ
ኸዝሁ ከረምሁ እያሉ ቢጨነቁ ይጠብቁ ብያቸው መጣሁ” አላት።
“ኸነማይ?” አለች፣ ምንትዋብ ተገርማ። ከነማይ ማን መልዕክት
ሊልክላት እንዲሚችል መገመት አቅቷት።
“አዎ... ዘመድ ልኮኝ ነው አሉ። የተጠቀለለ ነገር ይዘዋል። “ለእቴጌ በጃቸው በቀር ለሌላ እንዳትሰጥ ብለው አስምለውኝ ነው ያመጣሁት ይላሉ።”
የማናቸው መነኩሴ? እያለች ትንሽ ካሰበች በኋላ፣ “ይግቡ!" አለችው።
አዛዥ አርከሌድስ እጅ ነስቶ ወጣ። ጥቂት ቆይቶ በእሱ መሪነት
ቆብ የደፉ፣ ረጅምና ሰፊ ቀሚስ ያጠለቁ፣ ሽማግሌ ሰው ገብተው
መሬት ሊስሙ ሲያጎነብሱ፣ “ግድ የለም አባቴ ይቀመጡ” አለቻቸው፣ ምንትዋብ።
ፈንጠር ብለው ወንበር ላይ ተቀመጡ።
“አባቴ ኸየት መጡ? ደሞስ ማን ልኮዎት ነው የመጡ?” አለቻቸው። መነኩሴው ከተቀመጡበት ተነሥተው ለጥ ብለው እጅ ነሱ። “እቴጌ ዝናዎን ስሰማ ቆይቸ ዛሬ እርሶን ለማየት ያበቃችኝ ኪዳነ ምረት
ምስጋና ይግባት። እቴጌ ኸነማይ ነው የመጣሁ። ደፈጫ ኪዳነ ምረት ስለት ነበረኝና እሱን ላደርስ መኸዴ ነው ብየ ስነሳ አንድ ኸኛ ዘንድ ሚመላለሱ ሰው፣ '
እኼን ለእቴጌ እንደምንም ብለው አድርሱልኝ። ዐደራ በእጅ ይስጡልኝ። ዘመድ ነኝ ቢሉኝ አመንኳቸው።”
“ሰውየው ማን ይባለሉ?”
“እቴጌ ዕቃውን ሲያዩ ማን እንደሆንሁ ያቃሉ ብለውኛል” ብለው ጥቅሉን አሳዩ።
ምንትዋብ፣ አርከሌድስን፣ “ተቀበልና ፍታው” አለችው።
“እቴጌ ኸርሶ በቀር ለሌላ አትስጥ ተብያለሁ” አሉ፣ መነኩሴው፣
ብድግ ብለው።
“ይቀመጡ... ይስጡትና እኔ ፈታዋለሁ።”
ጥቅሉን ለአርከሌድስ ሲሰጡት ተቀብላ ስትፈታው ዐራት ማዕዘን
እንጨት ላይ የተሣለ የራሷ ምስል ነው። ነጠላ ተከናንባ ወፍታ ጊዮርጊስ ደጀሰላም ላይ ነው። መብረቅ የመታት ያህል ክው ብላ ቀረች።
መነኩሴው የፊቷን መለዋወጥ አይተው ደነገጡ። ከተቀመጡበት
ተነሱ። “እቴጌ... ክፉ ነገር ኑሯል?” ሲሉ ጠየቋት።
የለ፣ ደግ ነው። ብቻ ያልጠበቅሁት ነገር ሁኖብኝ ነው። የላክሁ
ሰውየ ስማቸው ማነው ነበር ያሉኝ?”.
ስማቸውን ስንኳ አላወቅሁም። እኔ ብዙ ግዝየን ኸሰው ስለማልገናኝ
ስለሰዎች እምብዛም አላውቅም። 'እነማይ ለጉዳይ መጠቼ፣ ጐንደር“
ይኸዳሉ ሲሉ ብሰማ ተላኩኝ ብየ ነው። ለእቴጌም ዘመድ ነኝ። የእቴጌ አያቶች እኮ ትውልዳቸው ኸዝሁ ኸኛው ዘንድ ነው ቢሉኝ ምን ከፋኝ ብየ ይዤ መጣሁ።”
“ወደ እነማይ በቅርቡ ይመለሳሉ?”
“ለርሶ መልክቴን ካደረስሁ እንግዲህ ነገ እነሳለሁ።”
“እንግዲያማ ደሕና ግቡ። ለላኩዎም ሰው ባክዎን ወደ ጐንደር ብቅ ይበሉ። እንደርሶ ያለ ሠዓሊ ፈልጋለሁ ይበሉልኝ” አለቻቸው።
👍8
ወደ አርከሌድስ ዞራ ለመነኩሴውአስፈላጊው
እንዲደረግላቸው ነግራው አሰናበተቻቸው። እነሱ ከሄዱ በኋላ፣ ሥዕሉን ደግማ ደጋግማ አየችው። ሥዕሉን የላከላት ሰው ማን ሊሆን እንደሚችል
መገመት አቃታት። ለቀናት፣ ለሳምንታትና ለወራት በነገሩ ስትጨነቅ፣ ስታወጣና ስታወርድ ቆየች። መልስ ልታገኝለት ግን አልቻለችም።
ሆኖም እያደር ነገሩ ከነከናት። የመልዕክቱ ትርጉም አልገባ አላት። ሕይወቷ የተለየ መልክ ሲይዝ፣ ትርጉም እያገኘ ሲመጣ እንደዚህ ያለ ነገር መከሠቱ ገረማት፣ ተንኮል ይሆን ብላ አወጣች አወረደች። ግና
የምን ተንኮል? ስለምንስ? በኔና በኢያሱ መኻል የመጣ ነው? ግና
እንዴት ያለ ሠዓሊ ነው? እኼን ዓይነቱን ሠዓሊማ ፈልጌ አስፈልጌ
ነው ማስመጣት ያለብኝ፡፡ ቤተክሲያን ላሰራ ፈልግ የለ? ያን ግዝየ ይጠቅመኛል እያለች ለወራት አወጣች አወረደች።..
✨ይቀጥላል✨
እንዲደረግላቸው ነግራው አሰናበተቻቸው። እነሱ ከሄዱ በኋላ፣ ሥዕሉን ደግማ ደጋግማ አየችው። ሥዕሉን የላከላት ሰው ማን ሊሆን እንደሚችል
መገመት አቃታት። ለቀናት፣ ለሳምንታትና ለወራት በነገሩ ስትጨነቅ፣ ስታወጣና ስታወርድ ቆየች። መልስ ልታገኝለት ግን አልቻለችም።
ሆኖም እያደር ነገሩ ከነከናት። የመልዕክቱ ትርጉም አልገባ አላት። ሕይወቷ የተለየ መልክ ሲይዝ፣ ትርጉም እያገኘ ሲመጣ እንደዚህ ያለ ነገር መከሠቱ ገረማት፣ ተንኮል ይሆን ብላ አወጣች አወረደች። ግና
የምን ተንኮል? ስለምንስ? በኔና በኢያሱ መኻል የመጣ ነው? ግና
እንዴት ያለ ሠዓሊ ነው? እኼን ዓይነቱን ሠዓሊማ ፈልጌ አስፈልጌ
ነው ማስመጣት ያለብኝ፡፡ ቤተክሲያን ላሰራ ፈልግ የለ? ያን ግዝየ ይጠቅመኛል እያለች ለወራት አወጣች አወረደች።..
✨ይቀጥላል✨
👍4
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሦስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....ወደ ሲዳሞ በስተርጅና ዕድሜዬ ብቅ ማለት አስባለሁ፡፡» ካለ በኋላ ወደ ሃምሳ አለቃው ቀና በማለት ፈገግ እያለ
«ግን ደግሞ ከሀገሬ በፊትእኔ ቀድሜ ካረጀሁ » አለው
«አልገባኝም::»
«የሀገር እርጅና፡፡»
አስቻለው ወደ መሬት አቀረቀረና ራሱን ወዘወዘ አውቆም ይሁን ሳያውቅ ከንፈሩን ነከሰ፡፡ ስሮቹ በግንባሩ ላይ ተገተሩ። ፊቱ ተከፋ፡፡
«አስረዳኛ የኔ ወንድም አለው»
የሃምሳ አለቃ ክንዶቹን አቆላልፎ
ጠረጴዛውን በመደገፍ አስቻለውን እየተመለከተ።
«ሀገር በገዳዮቿ መዳፍ ወስጥ እስከ ገባኝ ድረስ ምናልባት እንደ ሰው አትቀበር እንደሆነ እንጂ ማርጀት ቀርቶ ልትሞትም ትችላለች» አለ አስቻለው ፊቱ ክፍት እያለውና ጣሪያ ጣሪያ እያየ፡፡
«ስትል?» ሲል ጠየቀው የሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ፡ የአስቻለው አነጋገር ሚስጥሩ ለጊዜው ባይገባውም ግን ደግሞ በውስጡ ብዙ ነገር ስለመሆኑ ከወዲሁ ገምቷል።
«አየህ ሃምሳ አለቃ!» ሲል ቀጠለ እስቻለው፡፡ በአንድ ሀገር ውስጥ ያሉ የህዝብና መንግስት ከተኮራረፈ ምድርና ሰማያዋም ይቀያየማሉ። ያኔ ከዜጎቿ ልብ
ውስጥ ተስፋ ይጠፋል፡፡ ተስፋ የሌለበው ሕዝብ ጭካኔ ይወልዳል።በተለይ ደሃ ከጨከነ
ጠላት የሚያደርገው የገዛ ሀገሩን ነው፡፡ አምባገነኖች የቱንም ያክል
ጡንቻቸው ቢፈረጥም ድሀን ማስተዳደርና መቆጣጠር አይችሉም፡፡ እንዲያውም
በቁጣው እነሱንም ያጠፋቸዋል፡፡ ያኔ ገዢና ተጎዢ አይኖርምና 'ጥፋት ይነግሳል::በዚህ ጊዜ ሀገር መታመም ትጀምራለች። ታዲያ ይህ ከሆነ ሀገር አልሞተችም፣?
የሃምሣ አለቃ ሲል ጠየቀው።
የሃምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ ባላሰበውና አስቦትም በማያውቅ የተለየ እሳቤ ወስጥ ገባ፡፡ አንዳች አስፈሪ ስሜት ውስጥ ገባ። አንዳች አስፈሪ ስሜት መጣበት እስከዛሬም እንደ ሰው ስለመኖሩ ተጠራጠረ። ፍርሀትና ጭንቀትም አደረበት። በረጅሙ ተነፈሰና
«አስደነገጥከኝ አስቻለው» አለው፡፡
«ሊያስፈራም ሊያስደነግጥም ይችላል ሃምሣ አለቃ። በአሁኑ ሠዓት ሀገራችን ታማለች። ህመም ደግሞ በቶሉ ያስረጃል፡፡ ከሐገሬ በፊት እኔ ካረጀሁ ያልኩህም በዚህ ምክንያት ነው፡፡ አለና አስቻለው የሃምሳ አለቃን ትኩር ብሎ
ተመለከተው።
«ይህ ገባኝ አስቻለው አለና የሃምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ እንቆቅልሽ የሆነብኝ ግን ለምን ከዚያ ወዲህ ወደ ዲላ ላለመሄድ እንደነሰንክ ነው፡፡ ምናልባት
ይህም ምስጢር ይኖረው?» ሲል ፈራ ተባ እያለ ጠየቀው።
«ምስጢር የለውም፡፡ እኔ ግን መሄድ አልፈልግም::»
«አይመስለኝም አስቻለው፣ ይህ ውሳኔህ ምስጢር ሳይኖረው አይቀርም፡፡አይዞህ ምስጢር ቢኖረውም በበኩሌ እጠብቅልሃለሁና ንገረኝ፡፡» አለው።
«ወታደር አይደለህ! ለምስጢርማ ማን ብሎህ» አለና አስቻለው ፈገግ አለ፡፡
«ሙያዬ ስለሆነ ሳይሆን ባአንተ በመታመን።»
አስቻለው ጭንቅ አለው። የሃምሳ አለቃው ጥያቄ ከልቧ የመነጨ መሆኑ ይገባዋል ግን ደግሞ የሆዱን ምስጢር ለማንም ላለመናገር ወስኗል የሃምሳ አለቃው ልመና ግን መንፈሱን ወጥሮ ያዘው።ወደ ጣርያ ወደ መሬት ጎንበስ ቀና ካለ በኋላ
በቅድምያ በረጅሙ ተነፈሰ።
የሀምሳ አለቃውንም አየት ሲያደርገው በፊቱ ላይ የጭንቅ ስሜት አነበበበት። መጨነቁም ስለ እሱ መሆኑ ገባው። ከዚያ በኋላ ፍንጭ ሊሰጠው ፈለገ።
«አየህ ሃምሳ አለቃ! እኔ በአሁኑ ሰዓት ወደ ዲላ ብሄድ ያለ ጊዜዋ
የምትረግፍ አበባ አለች፡፡» አለና እንባው ከዓይኑ ላይ ዝርግፍ አለ፡፡
«እንዴት»
«አበባ የምልህ በእርግጥ ተክል አደለችም። ሔዋን ተስፋዬ የምትባል የሰው ልጅ ናት:: የምወዳት የምትወደኝ፣ የምሳሳላት የምትሳሳልኝን የመጀመርያ ፍቅረኛዩና እጮኛዬ ነበረች፡ ልንጋባ ሁለት ወር ሲቀረን ነበር እኔ ድንገት ወደዚህ ወደ አስመራ የመጣሁት።አሁን ግን ይህው እንደምታየኝ ግማሽ አካሌ ከጥቅም ውጭ ሆኗል ያለ ጊዜዋ ትረግፋለች የምልህም ያቺ አበባ እንዲህ ሁኜ ብታየኝ
የሚፈጠርባት፣ የስሜት ስቃይ ስለማውቅ ነው፡፡ እንደኔ እግሯ ባይቆረጥ እንኔ ፊቷ ባይጠበስ! እንደኔ ጆሮዋ ባይበላሽ፣ እንደኔ ዓይኗ ባይጠፋ እኔን በዚህ ሁኔታ
ካየች ግን በንዴት በቁጭት በብስጭትና በፀፀት የአእምሮ ህመምተኛ ትሆንብኛለች ብዬ እሰጋለሁ። ታዲያ ይህን እያወኩ ሄጄ የዚያችን አበባ ህይወት ላበላሸው ሃምሳ አለቃ?» አለውና በጉንጩ ላይ ይንቆረቆር የነበረ እንባውን በእጁ መዳፍ ሙሉ ሙዥቅ አድርጎ ጠረገው።
«አታልቅስ የኔ ወንድም!» አለው ሃምሣ አለቃ እሱም ዓይኑ በእንባ
እየሞላ።
«እኔማ ገና ብዙ ብዙ አለቅሳለሁ ሀምሳ አስቃ! እኔ ዕድለ ቢሱ ያቺን እድለ ቢስ አድርጊያት ቀርቻለሁ:: ስለ ሔዋን ተስፋዩ ገና ብዙ አለቅሳለሁ::በህይወት እስካለሁ ልረሳት አልችልምና ሳለቅስ እኖራለሁ፡፡» አለና አስቻለው
አሁንም እህህህህ …! በማለት መላ ሰውነቱ እስኪንቀጠቀጥ ድረስ በለቅሶ ሲቃ ተርገፈገፈ።
“ምናልባት ትጠየፈኛለች ብለህ ሰግተህ ይሆን የኔ ወንድም?» ሲል ሃምሣ አሐቃ የራሱንም አይን እየጠረገ ጠየቀው።
«ፍጹም ሀምሳ አለቃ! የኔዋ ሔዋን መልኳ አበባ እንደሚመስል ሁሉ
ትጠየፈኛለች ብዬ አይደለም፡፡ የኔዋ ሔዋን እንዲህ ያለ ተፈጥሮ የላትም። በራሴ በኩል ግን ከእንግዲህ እኔ ለእሷ አልገባም ብዬ ወስኛለሁ።» አለ እያለቀሰ።
“ታዲያ እሷ እየጠበቀችህ ቢሆንስ?»
«ተስፋ እንድትቆርጥ ብዩ የበኩሌን አንድ ርምጃ ወስጃለሁ። የምትኖረው በኔ ደመወዝ ስለነበር እንዲቋረጥባት ብዬ የመንግስት ስራ ለቅቄ በአንድ የፈረንጆች
ግብረ ሰናይ ድርጅት ክሊኒክ ውስጥ በአስተርጓሚነት ተቀጥሬአለሁ::»
«ምናልባት ርሀብ ላያሽንፋት ቢችልስ?»
«ይህ እኔንም ያሰጋኛል። ግን ልጅ ናትና ከመቆየት ሀሳቧን ብትቀይር
እያልኩ እጓጓለሁ:: በዚያ ላይ ደግሞ ገና እኔ እዚያው እያለሁ ሊድሯትና ሊያገቧትም እያሰቡ የሚያንዣብበ ሰዎች ነበሩና በእነሱ ጫና ተሸንፋ አዲስ
ህይወት ብትጀምር እያልኩም እፀልያለሁ::»
የሃምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ የአስቻለውን ምኞትና ሃሳብ ሲሰማ ቆይቶ ወደ ዲላ ላለመሄድ የወሰኑበት ምክንያት ሲገባው በራሱ ውስጥ ያለው የመንፈስ ቁስል አመመውና ለአስቻለው ይገልፅለት ዘንድ ስሜቱ ገፋፋው።
«ስማ እስቻለው፡፡» አለው ፍዝዝ ትክዝ ብሎ እየተመለከተው እኔም እንዳተው ተገድጄ ወደዚህ ሀሄገር የመጣሁ ነኝ መጥቼ የፈፀምኩት ነገር ቢኖር ሰው መግደል ነው።እላዬ ላይ የምታየው የሃምሣ አለቅነት መአረግ የተሰጠኝም ሰው በመግደሌ ነው። የገደልኩት ደሞ የሀገሬን ልጆች ወንድሞቼን ነው ሶስት አራት ገድዬ ከሆነ በዛው መጠን በርካታ ዘመድ አዝማዶቻቸውን አስለቅሻለሁ አሳዝኛለሁ በዚህ ስራዬ ደግም ተሸልሜበታለሁ። ታድያ እኔ ይሄን ያህል የህሊና እዳ ተሸክሜ ወደ ሃገሬ ልገባ ስቸኩል አንተ ልታክም መተህ ራስክ ከቆሰልክ ልትረዳ
መጥተህ ራስህ በተጎዳህ ልትጠግን መጥተህ ራስክ ከተሰበርክ ምን የህሊና የፀፀት አለብህና ምን የሚያሳፍር ነገር ሰርተሃልና ከዚህ አይነት አሳዛኝ ውሳኔ ላይ ልትደርስ ቻልክ?» ሲል ጠየቀው።
«ሀሳብህን አደንቃለሁ ሃምሳ አለቃ!» ሲል ጀመረ አስቻለው «ልዩነቱ ግን አንተ የገደልካቸው ኢትዮጵያውያን ሞተው አርፈዋል። ቤተሰቦቻቸውም እርማቸውን አውተው ተገላግለዋል።ፀፀቴ ያለው በአንተ ልብ ብቻ ነው።
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ሦስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....ወደ ሲዳሞ በስተርጅና ዕድሜዬ ብቅ ማለት አስባለሁ፡፡» ካለ በኋላ ወደ ሃምሳ አለቃው ቀና በማለት ፈገግ እያለ
«ግን ደግሞ ከሀገሬ በፊትእኔ ቀድሜ ካረጀሁ » አለው
«አልገባኝም::»
«የሀገር እርጅና፡፡»
አስቻለው ወደ መሬት አቀረቀረና ራሱን ወዘወዘ አውቆም ይሁን ሳያውቅ ከንፈሩን ነከሰ፡፡ ስሮቹ በግንባሩ ላይ ተገተሩ። ፊቱ ተከፋ፡፡
«አስረዳኛ የኔ ወንድም አለው»
የሃምሳ አለቃ ክንዶቹን አቆላልፎ
ጠረጴዛውን በመደገፍ አስቻለውን እየተመለከተ።
«ሀገር በገዳዮቿ መዳፍ ወስጥ እስከ ገባኝ ድረስ ምናልባት እንደ ሰው አትቀበር እንደሆነ እንጂ ማርጀት ቀርቶ ልትሞትም ትችላለች» አለ አስቻለው ፊቱ ክፍት እያለውና ጣሪያ ጣሪያ እያየ፡፡
«ስትል?» ሲል ጠየቀው የሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ፡ የአስቻለው አነጋገር ሚስጥሩ ለጊዜው ባይገባውም ግን ደግሞ በውስጡ ብዙ ነገር ስለመሆኑ ከወዲሁ ገምቷል።
«አየህ ሃምሳ አለቃ!» ሲል ቀጠለ እስቻለው፡፡ በአንድ ሀገር ውስጥ ያሉ የህዝብና መንግስት ከተኮራረፈ ምድርና ሰማያዋም ይቀያየማሉ። ያኔ ከዜጎቿ ልብ
ውስጥ ተስፋ ይጠፋል፡፡ ተስፋ የሌለበው ሕዝብ ጭካኔ ይወልዳል።በተለይ ደሃ ከጨከነ
ጠላት የሚያደርገው የገዛ ሀገሩን ነው፡፡ አምባገነኖች የቱንም ያክል
ጡንቻቸው ቢፈረጥም ድሀን ማስተዳደርና መቆጣጠር አይችሉም፡፡ እንዲያውም
በቁጣው እነሱንም ያጠፋቸዋል፡፡ ያኔ ገዢና ተጎዢ አይኖርምና 'ጥፋት ይነግሳል::በዚህ ጊዜ ሀገር መታመም ትጀምራለች። ታዲያ ይህ ከሆነ ሀገር አልሞተችም፣?
የሃምሣ አለቃ ሲል ጠየቀው።
የሃምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ ባላሰበውና አስቦትም በማያውቅ የተለየ እሳቤ ወስጥ ገባ፡፡ አንዳች አስፈሪ ስሜት ውስጥ ገባ። አንዳች አስፈሪ ስሜት መጣበት እስከዛሬም እንደ ሰው ስለመኖሩ ተጠራጠረ። ፍርሀትና ጭንቀትም አደረበት። በረጅሙ ተነፈሰና
«አስደነገጥከኝ አስቻለው» አለው፡፡
«ሊያስፈራም ሊያስደነግጥም ይችላል ሃምሣ አለቃ። በአሁኑ ሠዓት ሀገራችን ታማለች። ህመም ደግሞ በቶሉ ያስረጃል፡፡ ከሐገሬ በፊት እኔ ካረጀሁ ያልኩህም በዚህ ምክንያት ነው፡፡ አለና አስቻለው የሃምሳ አለቃን ትኩር ብሎ
ተመለከተው።
«ይህ ገባኝ አስቻለው አለና የሃምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ እንቆቅልሽ የሆነብኝ ግን ለምን ከዚያ ወዲህ ወደ ዲላ ላለመሄድ እንደነሰንክ ነው፡፡ ምናልባት
ይህም ምስጢር ይኖረው?» ሲል ፈራ ተባ እያለ ጠየቀው።
«ምስጢር የለውም፡፡ እኔ ግን መሄድ አልፈልግም::»
«አይመስለኝም አስቻለው፣ ይህ ውሳኔህ ምስጢር ሳይኖረው አይቀርም፡፡አይዞህ ምስጢር ቢኖረውም በበኩሌ እጠብቅልሃለሁና ንገረኝ፡፡» አለው።
«ወታደር አይደለህ! ለምስጢርማ ማን ብሎህ» አለና አስቻለው ፈገግ አለ፡፡
«ሙያዬ ስለሆነ ሳይሆን ባአንተ በመታመን።»
አስቻለው ጭንቅ አለው። የሃምሳ አለቃው ጥያቄ ከልቧ የመነጨ መሆኑ ይገባዋል ግን ደግሞ የሆዱን ምስጢር ለማንም ላለመናገር ወስኗል የሃምሳ አለቃው ልመና ግን መንፈሱን ወጥሮ ያዘው።ወደ ጣርያ ወደ መሬት ጎንበስ ቀና ካለ በኋላ
በቅድምያ በረጅሙ ተነፈሰ።
የሀምሳ አለቃውንም አየት ሲያደርገው በፊቱ ላይ የጭንቅ ስሜት አነበበበት። መጨነቁም ስለ እሱ መሆኑ ገባው። ከዚያ በኋላ ፍንጭ ሊሰጠው ፈለገ።
«አየህ ሃምሳ አለቃ! እኔ በአሁኑ ሰዓት ወደ ዲላ ብሄድ ያለ ጊዜዋ
የምትረግፍ አበባ አለች፡፡» አለና እንባው ከዓይኑ ላይ ዝርግፍ አለ፡፡
«እንዴት»
«አበባ የምልህ በእርግጥ ተክል አደለችም። ሔዋን ተስፋዬ የምትባል የሰው ልጅ ናት:: የምወዳት የምትወደኝ፣ የምሳሳላት የምትሳሳልኝን የመጀመርያ ፍቅረኛዩና እጮኛዬ ነበረች፡ ልንጋባ ሁለት ወር ሲቀረን ነበር እኔ ድንገት ወደዚህ ወደ አስመራ የመጣሁት።አሁን ግን ይህው እንደምታየኝ ግማሽ አካሌ ከጥቅም ውጭ ሆኗል ያለ ጊዜዋ ትረግፋለች የምልህም ያቺ አበባ እንዲህ ሁኜ ብታየኝ
የሚፈጠርባት፣ የስሜት ስቃይ ስለማውቅ ነው፡፡ እንደኔ እግሯ ባይቆረጥ እንኔ ፊቷ ባይጠበስ! እንደኔ ጆሮዋ ባይበላሽ፣ እንደኔ ዓይኗ ባይጠፋ እኔን በዚህ ሁኔታ
ካየች ግን በንዴት በቁጭት በብስጭትና በፀፀት የአእምሮ ህመምተኛ ትሆንብኛለች ብዬ እሰጋለሁ። ታዲያ ይህን እያወኩ ሄጄ የዚያችን አበባ ህይወት ላበላሸው ሃምሳ አለቃ?» አለውና በጉንጩ ላይ ይንቆረቆር የነበረ እንባውን በእጁ መዳፍ ሙሉ ሙዥቅ አድርጎ ጠረገው።
«አታልቅስ የኔ ወንድም!» አለው ሃምሣ አለቃ እሱም ዓይኑ በእንባ
እየሞላ።
«እኔማ ገና ብዙ ብዙ አለቅሳለሁ ሀምሳ አስቃ! እኔ ዕድለ ቢሱ ያቺን እድለ ቢስ አድርጊያት ቀርቻለሁ:: ስለ ሔዋን ተስፋዩ ገና ብዙ አለቅሳለሁ::በህይወት እስካለሁ ልረሳት አልችልምና ሳለቅስ እኖራለሁ፡፡» አለና አስቻለው
አሁንም እህህህህ …! በማለት መላ ሰውነቱ እስኪንቀጠቀጥ ድረስ በለቅሶ ሲቃ ተርገፈገፈ።
“ምናልባት ትጠየፈኛለች ብለህ ሰግተህ ይሆን የኔ ወንድም?» ሲል ሃምሣ አሐቃ የራሱንም አይን እየጠረገ ጠየቀው።
«ፍጹም ሀምሳ አለቃ! የኔዋ ሔዋን መልኳ አበባ እንደሚመስል ሁሉ
ትጠየፈኛለች ብዬ አይደለም፡፡ የኔዋ ሔዋን እንዲህ ያለ ተፈጥሮ የላትም። በራሴ በኩል ግን ከእንግዲህ እኔ ለእሷ አልገባም ብዬ ወስኛለሁ።» አለ እያለቀሰ።
“ታዲያ እሷ እየጠበቀችህ ቢሆንስ?»
«ተስፋ እንድትቆርጥ ብዩ የበኩሌን አንድ ርምጃ ወስጃለሁ። የምትኖረው በኔ ደመወዝ ስለነበር እንዲቋረጥባት ብዬ የመንግስት ስራ ለቅቄ በአንድ የፈረንጆች
ግብረ ሰናይ ድርጅት ክሊኒክ ውስጥ በአስተርጓሚነት ተቀጥሬአለሁ::»
«ምናልባት ርሀብ ላያሽንፋት ቢችልስ?»
«ይህ እኔንም ያሰጋኛል። ግን ልጅ ናትና ከመቆየት ሀሳቧን ብትቀይር
እያልኩ እጓጓለሁ:: በዚያ ላይ ደግሞ ገና እኔ እዚያው እያለሁ ሊድሯትና ሊያገቧትም እያሰቡ የሚያንዣብበ ሰዎች ነበሩና በእነሱ ጫና ተሸንፋ አዲስ
ህይወት ብትጀምር እያልኩም እፀልያለሁ::»
የሃምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ የአስቻለውን ምኞትና ሃሳብ ሲሰማ ቆይቶ ወደ ዲላ ላለመሄድ የወሰኑበት ምክንያት ሲገባው በራሱ ውስጥ ያለው የመንፈስ ቁስል አመመውና ለአስቻለው ይገልፅለት ዘንድ ስሜቱ ገፋፋው።
«ስማ እስቻለው፡፡» አለው ፍዝዝ ትክዝ ብሎ እየተመለከተው እኔም እንዳተው ተገድጄ ወደዚህ ሀሄገር የመጣሁ ነኝ መጥቼ የፈፀምኩት ነገር ቢኖር ሰው መግደል ነው።እላዬ ላይ የምታየው የሃምሣ አለቅነት መአረግ የተሰጠኝም ሰው በመግደሌ ነው። የገደልኩት ደሞ የሀገሬን ልጆች ወንድሞቼን ነው ሶስት አራት ገድዬ ከሆነ በዛው መጠን በርካታ ዘመድ አዝማዶቻቸውን አስለቅሻለሁ አሳዝኛለሁ በዚህ ስራዬ ደግም ተሸልሜበታለሁ። ታድያ እኔ ይሄን ያህል የህሊና እዳ ተሸክሜ ወደ ሃገሬ ልገባ ስቸኩል አንተ ልታክም መተህ ራስክ ከቆሰልክ ልትረዳ
መጥተህ ራስህ በተጎዳህ ልትጠግን መጥተህ ራስክ ከተሰበርክ ምን የህሊና የፀፀት አለብህና ምን የሚያሳፍር ነገር ሰርተሃልና ከዚህ አይነት አሳዛኝ ውሳኔ ላይ ልትደርስ ቻልክ?» ሲል ጠየቀው።
«ሀሳብህን አደንቃለሁ ሃምሳ አለቃ!» ሲል ጀመረ አስቻለው «ልዩነቱ ግን አንተ የገደልካቸው ኢትዮጵያውያን ሞተው አርፈዋል። ቤተሰቦቻቸውም እርማቸውን አውተው ተገላግለዋል።ፀፀቴ ያለው በአንተ ልብ ብቻ ነው።
👍10
ምናልባት ራስህን ይፈጅህ እንደሆነ እንጂ የሞቱትና ያዘኑት ግን ሁሉንም ተወጥተውታል
የኔ መሄድ ግን ወዳጆቼን እንደ እሳት ያቃጥላቸዋል፡፡ ቅድም
እንዳልኩህ በተለይ የኔዋ አበባ ትረግፍብኛለች፡፡ የህይወትን ጣዕም ታጣብኛለች።
የልጅነት ህይወቷ የስቃይና የመከራ ይሆንብኛል። እሷ ከእንግዲህ እኔን አግብታ የዚያ የቆራጣው፣ የዛያ የእውሩ፣ የዛያ የደንቆሮ ሚስት እየተባለች
እንድትኖር አልፈልግም፡፡ ሞቷል ብላ እንድትረሳኝ ብቻ ነው የምፈልግ ይህን መስዋትነት ልከፍልላት ይገባል። እወዳታለሁ እና ስቃይዋን አልፈልግም
አፈቅራታለሁና የህይወቷን መበላሸት አልሻም።» አለና አስቻለው አሁንም እንባውን በጉንጩ ላይ አንቆረቆረ።
የሀ'ምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ያአስቻለውን አኳኋን እየተመለከተ የእሱም ዓይን ያነባ ጀመር። አንድ ነገር ትዝ አለውና አስቻለውን ደግሞ ጠየቀው።
«ለመሆኑ ከልጅቷ ሌላ ዲላ ውስጥ የሚኖር ዘመድ የለክም?»
«ከእህትም ወድምም የሚበልጡ ጓደኞች ነበሩኝ ናፍቆትና ትዝታቸው
እድሜ ልክ የማይረሳ። አዎ እነሱን ሳስባቸውና ሳስታውሳቸ እኖራለሁ»
«ታዲያ ከእነሱ ዕድሜ ልክ ተለያይተህ መኖሩ አይቆጭህም?»
«ይበልጥ የሚያንገበግበኝ ግን ቀድሞ ነገር ከእነሱም ከሔዋንም ተለይቼ ወደዚህ ቦታ መምጣቴ ነው፡፡ ወዲህ እንድመጣ የተደረኩት በተንኰልና በደባ ነው።
ተናንቄአቸው ቢሆን! ምነው አሻፈረኝ ብዬ ቃታ ስበውብኝ ምነው አስረው በገረፉኝ ወይ ከስራ ተባርሬ እንደ ሌላው ወገኔ በርሃብ ሞቼ ቢሆን እያልኩ ሳስብ
ነው የሚቆጨኝ፡፡ ላይቀርልኝ ነገር
ስሸሽ መሞቴ ነው የሚያቃጥለኝ የአሁኑ ውሳኔማ የራሴ ስለሆነ ለምን ይቆጨኛል?የሁሉንም ናፍቆት፤ የሁሉንም ትዝታ
እችለዋለሁ። ገፍቶ ቢመጣብኝ ሀዘንና ለቅሶ ነው። እያዘንኩና እያለቀስኩ እኖራለሁ።
እነሱን ግን መልካም እንዲገጥማቸው እመኛለሁ፡፡» አለና ዓይኑን በመዳፉ አበስ አደረገ
«በእርጅና ዘመንህስ ጊዜ ለመሄድ ለምን አሰብክ?»
«ምናልባት ለኔዋ ሔዋን የማስበውና የምመኘው ሁሉ ተሳክቶላት ማየት የቻልኩ እንደሆነ ብዬ፡፡ በእርግጥም እኩያዋን አግብታ! ልጃች ወልዳ ለወግ ማእረግ አድርሳ ባገኛት የእሷን ከንፈር እንደሳምኩት ሁሉ የልጆቿን ጉንጮች ስሜአቸው ብሞት አጥንቴ በሰላም ሚተኛ አፋሩም የሚቀለኝ ይመስለኛል።»
የሀምሳ አስቀ መኮንን ዳርጌ የአስቻለው የፍቅር ፅናት! መልካም ምኞትና አርቆ አስተዋይነቱ እጅጉን ገርሞት ትክ ብሎ ሲመለከተው ድንገት ከቡና ቤቱ አንድ ሙዚቃ ተለቀቀ፡፡
ጊዜው ይርዘም እንጂ ማየት አይሻለሁ!
ጊዜው ይርዘም እንጂ ማየት አይሻለሁ፣
ሞት ካለየኝ በቀር በህይወት እያለሁ!
ሞት ካለየኝ በቀር በህይወት እያለሁ፡፡
አስቻለውና የሃምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ እርስ በእርስ ተያዩ። ነገሩ አጋጣሚ እንደሆነ ሁለቱም ገብቷቸዋል፡፡ ግን ደገሞ ረዘም ላለ ጊዜ እንባ እንዲራጩ አደረጋቸው።
የሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ዛሬ በዲላ ፖሊስ ጣቢያ ወስጥ ሔዋንን ከፊቱ አስቀምጦ በሀሳብ ወደ አስመራ በመኮብለል ይዞ የተመለሰው የትዝታ ጓዝ ይህን
ነበር፡፡ ደግነቱ ትዝታ የእውናዊ ክንውን ያህል ጊዜ አይወስድምና በትንሽ ደቂቃዎች ውስጥ ይሄን ሁሉ ቆይቶ ያነቃወም የራሱ ለቅሶ ነው፡፡ ድንገት «ህእ»የሚሰኝ የለቅሶ ትንታ ተናነቀው፡፡ እንባውም በጉንጮቹቿ ዧ ብሎ ወረዴ። ስሜቱን ከሔዋን ለመደበቅ አሰበና ወድያው ቀልጠፍ ብሎ።
«ምን እንዳስለቀስኝ ታውያለሽ?» አላት።
«ኧረ አላወኩም፡፡» አላችው ሔዋን እንባ ባቀረሩ ዓይኖቿ እየችው
«ልክ እንደ አንቺ ከፍቅረኛዬ ተለይቼ ስለምኖር እሷ ትዝ ብላኝ ነው፡፡» አላት እንባውን በመሀረብ እየጠራረገ፡፡ ሔዋን ለምን እትሄድላትም ልትለው ነበር፡፡
ግን ፈራችና ወደ መሬት አቀርቅራ እሷም ኣስቻለውን አስታወሳ ታለቅስ ጀመር።
«ለመሆን አሁን እንደት እየኖርሽ ነው?›› ሲል ጠየቃት ሀምሳ አለቃ።የዓለሙንና የመበራቱን ነገር እርግፍ አድርጎ ተወና ከአስቻለው ምኞትና ተስፋ አኳያ በምን ሁኔታ ላይ እንዳለች ለማወቅ ጓጓ፡፡
«ቀድሞ የአስቻለሁ ሰራተኛ፣ ዛሬ ደግሞ ለኔ ጓደኛ ከሆነች ትርፈ በጋሻው እምትባል ልጅ ጋር ቤት ተከራይተን አብረን እየኖርን ነው፡፡»
የሃምሳ አለቃ ያኔ አስቻለው ሞቷል ብላ ተስፋ እንድትቆርጥና ደሞዝ
ስታጣ ሌላ አማራጭ እንድትፈልግ ብዬ የመንግስት ስራ ለቅቄያለሁ ያለውን አስታውሶ «በምን ትተዳደራላችሁ?» ሲል ጠየቃት።
«በልሁ ተገኔ የሚባል የአስቻለው ጓደኛ እኔን በአውራጃው ግብርና ጽህፈት ቤት ውስጥ በተላላኪነት አስቀጥሮኛል፡፡ ለትርፌ ደግሞ መንቀሳቀሻ ወረት ሰጥቷት
ሻይና ዳቦ እየሸጠች እየተረዳዳን አብረን እንኖራለን፡፡»
«በዚህ ሁኔታ ለምን ያህል ጊዜ ቆያችሁ?»
«ሁለት ወር ይሆነናል፡፡ ትርፌ እሰው ቤት ተቀጥራ ትሰራ ነበር። እኔ ደግሞ ከእህቴ ጋር እኖር ነበር። ግን አህቴ ጋር ሳንስማማ ቀረን በልሁ ትርፌን ከሰው አውጥቶ አብረን እንድንኖር አደረገን።
«ባል ለማግባት አልሞከርሽም?»
«አስቻለውን ትቼ?» አለችው ዓይኖቿን በአይኖቹ ላይ ስክት አድርጋ።
«ምናልባት ባይመጣስ»
«ባይመጣም አላገባም'፡፡»
«ጭራሽ»
«ዕድሜ ልኬን፡፡»
ሀምሳ አለቃ አሁንም እንባው በዓይኑ ሞላ፡፡ የአሰሰቻለው ተስፋና ምኞት የመረብን ወንዝ አልተሻገረም በኤርትራ ሰማይ ላይ ተንሳፎ ቀርቷል። ሃምሳ አለቃ
እንባውን ጠርጎ ምራቄን ዋጥ አደረገና «ለመሆኑ በልሁ የሚባል የአስቻለው ጓደኛ እዚ ከታሰርሽ ወዲህ ጠይቆሻል?»ሲል ጠየቃት።
«አልሰማም መሰል እስካሁን አልመጣም»
ሃምሳ አለቃ መኮንን ከዚህ በኋላ ጊዜ ማጥፋት አልፈለገም ረዳቱን በደውል ጠራና ሔዋንን ወደ እስር ቤት አስወሰደ ረዴቱን እንደገና ጠራና ቀጭን ትዕዛዝ ሰጠው፡፡ «ይቺን ልጅ ሊጠይት በልሁ ተገኔ የሚባል ሰው ሲመጣ ከልጅቱ
ጋር ከመገናኘቱ በፊት ወደኔ አምጣልኝ፡፡" አለው፡፡...
💫ይቀጥላል💫
የኔ መሄድ ግን ወዳጆቼን እንደ እሳት ያቃጥላቸዋል፡፡ ቅድም
እንዳልኩህ በተለይ የኔዋ አበባ ትረግፍብኛለች፡፡ የህይወትን ጣዕም ታጣብኛለች።
የልጅነት ህይወቷ የስቃይና የመከራ ይሆንብኛል። እሷ ከእንግዲህ እኔን አግብታ የዚያ የቆራጣው፣ የዛያ የእውሩ፣ የዛያ የደንቆሮ ሚስት እየተባለች
እንድትኖር አልፈልግም፡፡ ሞቷል ብላ እንድትረሳኝ ብቻ ነው የምፈልግ ይህን መስዋትነት ልከፍልላት ይገባል። እወዳታለሁ እና ስቃይዋን አልፈልግም
አፈቅራታለሁና የህይወቷን መበላሸት አልሻም።» አለና አስቻለው አሁንም እንባውን በጉንጩ ላይ አንቆረቆረ።
የሀ'ምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ያአስቻለውን አኳኋን እየተመለከተ የእሱም ዓይን ያነባ ጀመር። አንድ ነገር ትዝ አለውና አስቻለውን ደግሞ ጠየቀው።
«ለመሆኑ ከልጅቷ ሌላ ዲላ ውስጥ የሚኖር ዘመድ የለክም?»
«ከእህትም ወድምም የሚበልጡ ጓደኞች ነበሩኝ ናፍቆትና ትዝታቸው
እድሜ ልክ የማይረሳ። አዎ እነሱን ሳስባቸውና ሳስታውሳቸ እኖራለሁ»
«ታዲያ ከእነሱ ዕድሜ ልክ ተለያይተህ መኖሩ አይቆጭህም?»
«ይበልጥ የሚያንገበግበኝ ግን ቀድሞ ነገር ከእነሱም ከሔዋንም ተለይቼ ወደዚህ ቦታ መምጣቴ ነው፡፡ ወዲህ እንድመጣ የተደረኩት በተንኰልና በደባ ነው።
ተናንቄአቸው ቢሆን! ምነው አሻፈረኝ ብዬ ቃታ ስበውብኝ ምነው አስረው በገረፉኝ ወይ ከስራ ተባርሬ እንደ ሌላው ወገኔ በርሃብ ሞቼ ቢሆን እያልኩ ሳስብ
ነው የሚቆጨኝ፡፡ ላይቀርልኝ ነገር
ስሸሽ መሞቴ ነው የሚያቃጥለኝ የአሁኑ ውሳኔማ የራሴ ስለሆነ ለምን ይቆጨኛል?የሁሉንም ናፍቆት፤ የሁሉንም ትዝታ
እችለዋለሁ። ገፍቶ ቢመጣብኝ ሀዘንና ለቅሶ ነው። እያዘንኩና እያለቀስኩ እኖራለሁ።
እነሱን ግን መልካም እንዲገጥማቸው እመኛለሁ፡፡» አለና ዓይኑን በመዳፉ አበስ አደረገ
«በእርጅና ዘመንህስ ጊዜ ለመሄድ ለምን አሰብክ?»
«ምናልባት ለኔዋ ሔዋን የማስበውና የምመኘው ሁሉ ተሳክቶላት ማየት የቻልኩ እንደሆነ ብዬ፡፡ በእርግጥም እኩያዋን አግብታ! ልጃች ወልዳ ለወግ ማእረግ አድርሳ ባገኛት የእሷን ከንፈር እንደሳምኩት ሁሉ የልጆቿን ጉንጮች ስሜአቸው ብሞት አጥንቴ በሰላም ሚተኛ አፋሩም የሚቀለኝ ይመስለኛል።»
የሀምሳ አስቀ መኮንን ዳርጌ የአስቻለው የፍቅር ፅናት! መልካም ምኞትና አርቆ አስተዋይነቱ እጅጉን ገርሞት ትክ ብሎ ሲመለከተው ድንገት ከቡና ቤቱ አንድ ሙዚቃ ተለቀቀ፡፡
ጊዜው ይርዘም እንጂ ማየት አይሻለሁ!
ጊዜው ይርዘም እንጂ ማየት አይሻለሁ፣
ሞት ካለየኝ በቀር በህይወት እያለሁ!
ሞት ካለየኝ በቀር በህይወት እያለሁ፡፡
አስቻለውና የሃምሣ አለቃ መኮንን ዳርጌ እርስ በእርስ ተያዩ። ነገሩ አጋጣሚ እንደሆነ ሁለቱም ገብቷቸዋል፡፡ ግን ደገሞ ረዘም ላለ ጊዜ እንባ እንዲራጩ አደረጋቸው።
የሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ዛሬ በዲላ ፖሊስ ጣቢያ ወስጥ ሔዋንን ከፊቱ አስቀምጦ በሀሳብ ወደ አስመራ በመኮብለል ይዞ የተመለሰው የትዝታ ጓዝ ይህን
ነበር፡፡ ደግነቱ ትዝታ የእውናዊ ክንውን ያህል ጊዜ አይወስድምና በትንሽ ደቂቃዎች ውስጥ ይሄን ሁሉ ቆይቶ ያነቃወም የራሱ ለቅሶ ነው፡፡ ድንገት «ህእ»የሚሰኝ የለቅሶ ትንታ ተናነቀው፡፡ እንባውም በጉንጮቹቿ ዧ ብሎ ወረዴ። ስሜቱን ከሔዋን ለመደበቅ አሰበና ወድያው ቀልጠፍ ብሎ።
«ምን እንዳስለቀስኝ ታውያለሽ?» አላት።
«ኧረ አላወኩም፡፡» አላችው ሔዋን እንባ ባቀረሩ ዓይኖቿ እየችው
«ልክ እንደ አንቺ ከፍቅረኛዬ ተለይቼ ስለምኖር እሷ ትዝ ብላኝ ነው፡፡» አላት እንባውን በመሀረብ እየጠራረገ፡፡ ሔዋን ለምን እትሄድላትም ልትለው ነበር፡፡
ግን ፈራችና ወደ መሬት አቀርቅራ እሷም ኣስቻለውን አስታወሳ ታለቅስ ጀመር።
«ለመሆን አሁን እንደት እየኖርሽ ነው?›› ሲል ጠየቃት ሀምሳ አለቃ።የዓለሙንና የመበራቱን ነገር እርግፍ አድርጎ ተወና ከአስቻለው ምኞትና ተስፋ አኳያ በምን ሁኔታ ላይ እንዳለች ለማወቅ ጓጓ፡፡
«ቀድሞ የአስቻለሁ ሰራተኛ፣ ዛሬ ደግሞ ለኔ ጓደኛ ከሆነች ትርፈ በጋሻው እምትባል ልጅ ጋር ቤት ተከራይተን አብረን እየኖርን ነው፡፡»
የሃምሳ አለቃ ያኔ አስቻለው ሞቷል ብላ ተስፋ እንድትቆርጥና ደሞዝ
ስታጣ ሌላ አማራጭ እንድትፈልግ ብዬ የመንግስት ስራ ለቅቄያለሁ ያለውን አስታውሶ «በምን ትተዳደራላችሁ?» ሲል ጠየቃት።
«በልሁ ተገኔ የሚባል የአስቻለው ጓደኛ እኔን በአውራጃው ግብርና ጽህፈት ቤት ውስጥ በተላላኪነት አስቀጥሮኛል፡፡ ለትርፌ ደግሞ መንቀሳቀሻ ወረት ሰጥቷት
ሻይና ዳቦ እየሸጠች እየተረዳዳን አብረን እንኖራለን፡፡»
«በዚህ ሁኔታ ለምን ያህል ጊዜ ቆያችሁ?»
«ሁለት ወር ይሆነናል፡፡ ትርፌ እሰው ቤት ተቀጥራ ትሰራ ነበር። እኔ ደግሞ ከእህቴ ጋር እኖር ነበር። ግን አህቴ ጋር ሳንስማማ ቀረን በልሁ ትርፌን ከሰው አውጥቶ አብረን እንድንኖር አደረገን።
«ባል ለማግባት አልሞከርሽም?»
«አስቻለውን ትቼ?» አለችው ዓይኖቿን በአይኖቹ ላይ ስክት አድርጋ።
«ምናልባት ባይመጣስ»
«ባይመጣም አላገባም'፡፡»
«ጭራሽ»
«ዕድሜ ልኬን፡፡»
ሀምሳ አለቃ አሁንም እንባው በዓይኑ ሞላ፡፡ የአሰሰቻለው ተስፋና ምኞት የመረብን ወንዝ አልተሻገረም በኤርትራ ሰማይ ላይ ተንሳፎ ቀርቷል። ሃምሳ አለቃ
እንባውን ጠርጎ ምራቄን ዋጥ አደረገና «ለመሆኑ በልሁ የሚባል የአስቻለው ጓደኛ እዚ ከታሰርሽ ወዲህ ጠይቆሻል?»ሲል ጠየቃት።
«አልሰማም መሰል እስካሁን አልመጣም»
ሃምሳ አለቃ መኮንን ከዚህ በኋላ ጊዜ ማጥፋት አልፈለገም ረዳቱን በደውል ጠራና ሔዋንን ወደ እስር ቤት አስወሰደ ረዴቱን እንደገና ጠራና ቀጭን ትዕዛዝ ሰጠው፡፡ «ይቺን ልጅ ሊጠይት በልሁ ተገኔ የሚባል ሰው ሲመጣ ከልጅቱ
ጋር ከመገናኘቱ በፊት ወደኔ አምጣልኝ፡፡" አለው፡፡...
💫ይቀጥላል💫
👍12
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...እንደ ሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ከትዝታ ጋር የተቀላቀለ አይሁን እንጂ መርዕድ እሽቴም በደረቅ ጭንቀት ተወጥሮ ነው ያረፈደው የጀመረው ደግሞ ጠዋት ሁለት ሰዓት በፊት፡፡ መኖሪያው በዜሮ ሁለት ቀበሌ የታችኛው ጥግ ሲሆን የሚያስተምረው ደግሞ የዲላ ከተማ የላይኛው ጫፍ
በሆነ ቀበሌውስጥ በማገኘው
የአፄ ዳዊት ትምህርት ቤት ውስጥ ነው። ሔዋንና ትርፊ የተከራዬት መንገዱ ላይ በመሆኑ ሲወጣም ሲወርድም ጎራ እያለ ይጠይቃቸው ነበር፡፡ ዛሬ ጠዋት ግን ወደ ሥራው ሲሄድ ያ ቤት በጠዋት ከውጭ ተዘግቶ አየው ወዴት እንደሄዱ የጎረቤት ስዎችን ሲጠይቅ ማታ ሲሆንና ሲባል ያመሸው ሁሉ ሁሉ የዝርዝር ተነገረው።
በሰማው ወሬ የተሰማው ድንጋጤ ጭራሽ ራስ ምታት ለቀቀበት። ዛሬ
ቢቸግረው ወደ በልሁ ቢሮ ሮጠ፡፡ ነገር ግን ዘንግቶ ነበር እንጂ በልሁ
ለመስክ ስራ ወጥቷል መስሪያ ቤት ደርሶ ይኸው ሲነግረው ያለ ውጤት ተመለሰ።
እንደገና ወደ ታፈሠ ቤት ላሮጥ አሰበ፡፡ ግን ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ክፍለ ጊዜ አስተምሮ ሌሎቹን ክፍለ ጊዜያት ነፃ እንደሆነ አስታወሰና በአንድ ፊት ስራውን
አጠናቆ ለመሄድ ወስኖ እየተጨነቀም ቢሆን ወደ ትምህርት ቤት አመራ፡
ልክ ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ሥራውን ጨርሶ ወደ ታፈሡ ቤት
በመገስገስ ላይ ሳለ አስፋልቱን አቋርጦ ሊያልፍ ሲል ከይርጋ ጨፌ አቅጣጫ ትመጣ የነበረች ቶዮታ መኪና ደጋግማ ክላክስ ስታደርግ ሰማ። ዞር ብሎ ሲመለከት የበልሁ የመስክ መኪና ናት:: በክላክስ ያስጠራውም ራሱ በልሁ ኖሯል፡፡ በአለበት ላይ ቆሞ መኪናዋን ጠበቀ።
«ዛሬ ስራ የለም እንዴ?» ሲል ጠየቀው በልሁ አጠገቡ ሲደርስ አንገቱን በመስኮት አውጥቶ መርዕድን እየተመለከተ፡፡
«እስቲ ና ውረድ!» አለ መርዕድ ፊቱ በድንጋጤ ጭምትርትር እንዳለ።በልሁም የመርዕድ ሁኔታ ገና ሲያየው እስደንግጦታል። «ምነው? ምን ሆነካል?
«ችግር አለ፡፡»
በልሁ ከመኪናዋ ላይ ዱብ ብሎ ወደ መርዕድ በመጠጋት ምንድን ነው ችግሩ? ሲል ጠየቀው።
«ሔዋን ታስራለች!»
«ምን አድርጋ?»
መርዕድ ከሰው የሰማውን በሙሉ ነገረው::
«ያምሀል እንዴ አንተ ሰው?»
«የነገሩኝን ነው እኔ የምነግርህ?»
“ከታሰረች ጠይቀሃታል?»
« አሁን ወዚያው እየሄድኩ ነበር፡፡»
ለነበሩበት ቦታ ፖሊስ ጣቢያው ቅርብ ነው፡፡ በልሁ ሾፈሩን ወደ ቤቱ እንዲሄድ አሰናበተውና ከመርዕድ ጋር ወደ ፖሊስ ጣቢያው ገሰገሱ፡፡ እርምጃቸው
ፈጣን ስለነበር ከአምስት ደቂቃ በላይ አልወሰደባቸውም።
ትርፌ ገና በጠዋት ለሔዋን ቁርስ ይዛ እንደሄደች አልተመለሰችም ኖሯል፡እንዲያውም በእስረኞች ግቢ እንድትገባ ተፈቅዶላት ኖሮ ፊት ለፊት ሔዋን ጋር አብረው ተቀምጠው በልሁና መርዕድን ከሩቅ ሲያዩአቸው ተንጫጬ «በልሁ! መርዕድ! በልሁ! መርዕድ!» በማለት።
በልሁና መርዕድ ጣቢያው በር ላይ እንደ ደረሱ አንድ ፖሊስ ጠጋ
አላቸውና ««ከእናንተ ወስጥ በልሁ ተገኒ የሚባል ማነው?» ሲል ጠየቃቸው፡፡
«እኔ!» አለው በልሁ በሌባ ጣቱ ወደ ራሱ እያመለከተ፡፡
«ሃምሳ አለቃ ይፈልጉሃል።»
«በሰላም?»
«አላወቅሁም አለና ፖሊስ ወደ እነ ሔዋን ዞር ብሎ አየት አደረገና ፊቱን ወደ በልሁ በመመለስ ከልጅቷ ጋር ሳይገናኝ ወደኔ አምጡት ነው ያሉት» አለው።
«ቢሮው የት ነው?» አለ በልሁ ቁና ቁና እየተነፈሰ፡፡
«ተከተለኝ! አለና ፖሊስ በልሁን ከፊት ከፊት እየመራ ወስዶ ካሃምሳ አለቃው ቢሮ አስገባው፡፡
የሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ጆሮግንዶቹን በእጆቹ ይዞ
ጠረጴዛው ላይ በማቀርተር ሀሳብ ውስጥ ገብቶ ሳለ ፖሊስ በልሁን ይዞ በመድረስ «አቶ በልሁ
እኒህ ናቸው አለው፡፡ ሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ለካ በልሁን ከተማ ውስጥ በዓይን ያወቀው ኖሯል:: እንዲያውም በአለባበስ፣ በተክለ ሰውነቱና አጠቃላይ አቋሙ
ያደንቀው የነበረ ሰው ሆኖ ሲያገኘው ‹‹በልሁ ተገኒ ማለት አንተ ኖረሀል እንዴ?
እያለ ብድግ ብሎ ጨበጠው::
«አዎ ነኝ» አለ በልሁ ቁና ቁና እየተነፈሰ፡፡
«ቁጭ በል እስቲ! ሁለቱም ፊት ለፊት ተቀመጡና ተፋጠጡ፡፡
«የተበሳጨህ ትመስላለህ!» አለው የሃምሣ አለቃ፡፡
«አዎ እጅግ በጣም ተናድጃለሁ፡፡
«ምነው?»
«የማትታሰር ሰው አስራችኋላ» አለው በልሁ ቁጭ እንዳለ በቀኝ
ሽንጡን በመያዝ ሃምሳ አለቃውን እየተመለከተ።
«ወንጀል ፈጽማ እንሆነስ» አለ ሃምሳ አለቃው ፈገግ እያለ።
«የተባለው ከሆነ አላምንም።» አለና በልሁ የሃምሳ አለቃውን ጠረጴዛ መታ መታ እያደረገ «ቀድሞ ነገር የተሰራ ሁሉ ወንጀለኛ የአሰረ ሁሉ ዳኛ ነው ብዬ ማመን ከተውኩ ቆይቼአለሁ።» አለው።
«አይፈረድብህም»
«አሁን ለምን ፈለከኝ።» ሲል በልሁ ዓይኑን ፈጠጥ አድርጎ ጠየቀው።
«ለብርቱ ጉዳይ !» አለና ሃምሳ አለቃ በረጅሙ ተንፍሶ "ግን አቶ በልሁ አሁን የምነግርህ ጉዳይ ሔዋን ለምትባል ልጅ ፈፅሞ መነገር የለበትም ባይሆን
ለአንተና ለቅርብ ጓደኞችህ ከነገርኳችሁ በኋላ አስባችሁበት የሚሆን ነገር ነው።"
«ምንድነው እሱ?»
«አስቻለው ፍስሀ የሚባል ጓደኛ እንደነበረህ ሰማው።»
«አሁንም አለኝ::»
«አብራችሁ ያላችሁ አይመስለኝም።»
«ከልቤ አይወጣምና ምንጊዜም አብረን የምንኖር ይመስለኛል»
«በአካል ማለቴ ነው፡፡»
«ክፉዎች አለያይተውናል፡፡ አሁን የትና በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ
አላውቅም።» ካለ በኋላ በልሁ «ለአንተ ማን ነገረህ? ሲል ጠየቀን
«በህይወት አለ ብልህ ታምናለህ?
«የት አገር?»
«እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ፡፡»
«ኦ?» አፉ ተከፍቶ ቀረ ዓይኖቹ በሃምሳ አለቃው ላይ ተተከሉ
«እስቲ ከሚቀርበህ ሰዎች ጋር በመሆን ተሰባሰቡልኝና ስለ እሱ ሁኔታ በጋራ ላናጋገራችሁ፡፡ እኔ የማውቀው ነገር አለኝ፡፡
«ዛሬ ማታ ቢሆንስ?»
«ይቻላል»
«ቦታና ሰአት ወስነው ተለያዩ፡፡»
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ፖሊስ ሆኖ ከተቀጠረ ጀምሮ አሁን
ያጋጠመውን ዓይነት አስደሳች ሥራ እግኝቶ አያውቅም። የሔዋንና በእሷ ምክንያት ተጣላን ያሉ ሰዎችን ጉዳይ እንደ የመንግስት ተቀጣሪነቱ ሳይሆን ልክ እንደ ራሱ
ገዳይ በተለየ ስሜትና ትኩረት ሊከታተለው ወሰነ።
የስራው የመጀመሪያ ዕቅድ የሔዋንን ድንግልና በሐኪም ማረጋገጥ ነበር።በእርግጥም ፈፀመው ሔዋን ያልተሟሸ ገላ ባለቤት ሆና አገኛት። የምስክር
ወረቀቱንም በእጁ ያዘ፡፡ ለምርመራው የሚያወመቹ በርካታ ፍንጮችን ከእነበልሁ አግኝቷል፡፡ የምርመራው ሂደት በዚያው አቅጣጫ እንዲጓዝ አድርጎ እቅድና
ስልቱንም ቀይሶታል፡፡ ስለ አስቻለው ሁኔታ ታፈሡን በልዑንና መርዕድን ሲያነጋግር ባመሽበት ሶስተኛ ቀን ላይ ዓለሙ መርጋንና መብራቴ ባዩን ሁለቱንም በአንድ ጊዜ ከቢሮው አስቀረባቸውና «ልብ ብላችሁ አድምጡኝ» ሲል ሀምሳ አለቃ አስጠነቀቃቸው፥ ዓለሙና መብራቴ ከፊቱ ተቀምጠው የሚሆኑት ሁኔታ በራሱ ውስጣቸውን ያስነብበዋል።
«ሔዋን ተስፋዬ የምትባል ሴት ወዳጃችሁ እንደሆነች ቃል በሰጣችሁበት ወረቀት ላይ ፊርማችሁን አኑራችኋል ነው ወይስ እይደለም?» ሲል ጠየቃቸው።
፡
፡
#ክፍል_አርባ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...እንደ ሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ከትዝታ ጋር የተቀላቀለ አይሁን እንጂ መርዕድ እሽቴም በደረቅ ጭንቀት ተወጥሮ ነው ያረፈደው የጀመረው ደግሞ ጠዋት ሁለት ሰዓት በፊት፡፡ መኖሪያው በዜሮ ሁለት ቀበሌ የታችኛው ጥግ ሲሆን የሚያስተምረው ደግሞ የዲላ ከተማ የላይኛው ጫፍ
በሆነ ቀበሌውስጥ በማገኘው
የአፄ ዳዊት ትምህርት ቤት ውስጥ ነው። ሔዋንና ትርፊ የተከራዬት መንገዱ ላይ በመሆኑ ሲወጣም ሲወርድም ጎራ እያለ ይጠይቃቸው ነበር፡፡ ዛሬ ጠዋት ግን ወደ ሥራው ሲሄድ ያ ቤት በጠዋት ከውጭ ተዘግቶ አየው ወዴት እንደሄዱ የጎረቤት ስዎችን ሲጠይቅ ማታ ሲሆንና ሲባል ያመሸው ሁሉ ሁሉ የዝርዝር ተነገረው።
በሰማው ወሬ የተሰማው ድንጋጤ ጭራሽ ራስ ምታት ለቀቀበት። ዛሬ
ቢቸግረው ወደ በልሁ ቢሮ ሮጠ፡፡ ነገር ግን ዘንግቶ ነበር እንጂ በልሁ
ለመስክ ስራ ወጥቷል መስሪያ ቤት ደርሶ ይኸው ሲነግረው ያለ ውጤት ተመለሰ።
እንደገና ወደ ታፈሠ ቤት ላሮጥ አሰበ፡፡ ግን ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ክፍለ ጊዜ አስተምሮ ሌሎቹን ክፍለ ጊዜያት ነፃ እንደሆነ አስታወሰና በአንድ ፊት ስራውን
አጠናቆ ለመሄድ ወስኖ እየተጨነቀም ቢሆን ወደ ትምህርት ቤት አመራ፡
ልክ ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ሥራውን ጨርሶ ወደ ታፈሡ ቤት
በመገስገስ ላይ ሳለ አስፋልቱን አቋርጦ ሊያልፍ ሲል ከይርጋ ጨፌ አቅጣጫ ትመጣ የነበረች ቶዮታ መኪና ደጋግማ ክላክስ ስታደርግ ሰማ። ዞር ብሎ ሲመለከት የበልሁ የመስክ መኪና ናት:: በክላክስ ያስጠራውም ራሱ በልሁ ኖሯል፡፡ በአለበት ላይ ቆሞ መኪናዋን ጠበቀ።
«ዛሬ ስራ የለም እንዴ?» ሲል ጠየቀው በልሁ አጠገቡ ሲደርስ አንገቱን በመስኮት አውጥቶ መርዕድን እየተመለከተ፡፡
«እስቲ ና ውረድ!» አለ መርዕድ ፊቱ በድንጋጤ ጭምትርትር እንዳለ።በልሁም የመርዕድ ሁኔታ ገና ሲያየው እስደንግጦታል። «ምነው? ምን ሆነካል?
«ችግር አለ፡፡»
በልሁ ከመኪናዋ ላይ ዱብ ብሎ ወደ መርዕድ በመጠጋት ምንድን ነው ችግሩ? ሲል ጠየቀው።
«ሔዋን ታስራለች!»
«ምን አድርጋ?»
መርዕድ ከሰው የሰማውን በሙሉ ነገረው::
«ያምሀል እንዴ አንተ ሰው?»
«የነገሩኝን ነው እኔ የምነግርህ?»
“ከታሰረች ጠይቀሃታል?»
« አሁን ወዚያው እየሄድኩ ነበር፡፡»
ለነበሩበት ቦታ ፖሊስ ጣቢያው ቅርብ ነው፡፡ በልሁ ሾፈሩን ወደ ቤቱ እንዲሄድ አሰናበተውና ከመርዕድ ጋር ወደ ፖሊስ ጣቢያው ገሰገሱ፡፡ እርምጃቸው
ፈጣን ስለነበር ከአምስት ደቂቃ በላይ አልወሰደባቸውም።
ትርፌ ገና በጠዋት ለሔዋን ቁርስ ይዛ እንደሄደች አልተመለሰችም ኖሯል፡እንዲያውም በእስረኞች ግቢ እንድትገባ ተፈቅዶላት ኖሮ ፊት ለፊት ሔዋን ጋር አብረው ተቀምጠው በልሁና መርዕድን ከሩቅ ሲያዩአቸው ተንጫጬ «በልሁ! መርዕድ! በልሁ! መርዕድ!» በማለት።
በልሁና መርዕድ ጣቢያው በር ላይ እንደ ደረሱ አንድ ፖሊስ ጠጋ
አላቸውና ««ከእናንተ ወስጥ በልሁ ተገኒ የሚባል ማነው?» ሲል ጠየቃቸው፡፡
«እኔ!» አለው በልሁ በሌባ ጣቱ ወደ ራሱ እያመለከተ፡፡
«ሃምሳ አለቃ ይፈልጉሃል።»
«በሰላም?»
«አላወቅሁም አለና ፖሊስ ወደ እነ ሔዋን ዞር ብሎ አየት አደረገና ፊቱን ወደ በልሁ በመመለስ ከልጅቷ ጋር ሳይገናኝ ወደኔ አምጡት ነው ያሉት» አለው።
«ቢሮው የት ነው?» አለ በልሁ ቁና ቁና እየተነፈሰ፡፡
«ተከተለኝ! አለና ፖሊስ በልሁን ከፊት ከፊት እየመራ ወስዶ ካሃምሳ አለቃው ቢሮ አስገባው፡፡
የሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ጆሮግንዶቹን በእጆቹ ይዞ
ጠረጴዛው ላይ በማቀርተር ሀሳብ ውስጥ ገብቶ ሳለ ፖሊስ በልሁን ይዞ በመድረስ «አቶ በልሁ
እኒህ ናቸው አለው፡፡ ሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ለካ በልሁን ከተማ ውስጥ በዓይን ያወቀው ኖሯል:: እንዲያውም በአለባበስ፣ በተክለ ሰውነቱና አጠቃላይ አቋሙ
ያደንቀው የነበረ ሰው ሆኖ ሲያገኘው ‹‹በልሁ ተገኒ ማለት አንተ ኖረሀል እንዴ?
እያለ ብድግ ብሎ ጨበጠው::
«አዎ ነኝ» አለ በልሁ ቁና ቁና እየተነፈሰ፡፡
«ቁጭ በል እስቲ! ሁለቱም ፊት ለፊት ተቀመጡና ተፋጠጡ፡፡
«የተበሳጨህ ትመስላለህ!» አለው የሃምሣ አለቃ፡፡
«አዎ እጅግ በጣም ተናድጃለሁ፡፡
«ምነው?»
«የማትታሰር ሰው አስራችኋላ» አለው በልሁ ቁጭ እንዳለ በቀኝ
ሽንጡን በመያዝ ሃምሳ አለቃውን እየተመለከተ።
«ወንጀል ፈጽማ እንሆነስ» አለ ሃምሳ አለቃው ፈገግ እያለ።
«የተባለው ከሆነ አላምንም።» አለና በልሁ የሃምሳ አለቃውን ጠረጴዛ መታ መታ እያደረገ «ቀድሞ ነገር የተሰራ ሁሉ ወንጀለኛ የአሰረ ሁሉ ዳኛ ነው ብዬ ማመን ከተውኩ ቆይቼአለሁ።» አለው።
«አይፈረድብህም»
«አሁን ለምን ፈለከኝ።» ሲል በልሁ ዓይኑን ፈጠጥ አድርጎ ጠየቀው።
«ለብርቱ ጉዳይ !» አለና ሃምሳ አለቃ በረጅሙ ተንፍሶ "ግን አቶ በልሁ አሁን የምነግርህ ጉዳይ ሔዋን ለምትባል ልጅ ፈፅሞ መነገር የለበትም ባይሆን
ለአንተና ለቅርብ ጓደኞችህ ከነገርኳችሁ በኋላ አስባችሁበት የሚሆን ነገር ነው።"
«ምንድነው እሱ?»
«አስቻለው ፍስሀ የሚባል ጓደኛ እንደነበረህ ሰማው።»
«አሁንም አለኝ::»
«አብራችሁ ያላችሁ አይመስለኝም።»
«ከልቤ አይወጣምና ምንጊዜም አብረን የምንኖር ይመስለኛል»
«በአካል ማለቴ ነው፡፡»
«ክፉዎች አለያይተውናል፡፡ አሁን የትና በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ
አላውቅም።» ካለ በኋላ በልሁ «ለአንተ ማን ነገረህ? ሲል ጠየቀን
«በህይወት አለ ብልህ ታምናለህ?
«የት አገር?»
«እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ፡፡»
«ኦ?» አፉ ተከፍቶ ቀረ ዓይኖቹ በሃምሳ አለቃው ላይ ተተከሉ
«እስቲ ከሚቀርበህ ሰዎች ጋር በመሆን ተሰባሰቡልኝና ስለ እሱ ሁኔታ በጋራ ላናጋገራችሁ፡፡ እኔ የማውቀው ነገር አለኝ፡፡
«ዛሬ ማታ ቢሆንስ?»
«ይቻላል»
«ቦታና ሰአት ወስነው ተለያዩ፡፡»
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ፖሊስ ሆኖ ከተቀጠረ ጀምሮ አሁን
ያጋጠመውን ዓይነት አስደሳች ሥራ እግኝቶ አያውቅም። የሔዋንና በእሷ ምክንያት ተጣላን ያሉ ሰዎችን ጉዳይ እንደ የመንግስት ተቀጣሪነቱ ሳይሆን ልክ እንደ ራሱ
ገዳይ በተለየ ስሜትና ትኩረት ሊከታተለው ወሰነ።
የስራው የመጀመሪያ ዕቅድ የሔዋንን ድንግልና በሐኪም ማረጋገጥ ነበር።በእርግጥም ፈፀመው ሔዋን ያልተሟሸ ገላ ባለቤት ሆና አገኛት። የምስክር
ወረቀቱንም በእጁ ያዘ፡፡ ለምርመራው የሚያወመቹ በርካታ ፍንጮችን ከእነበልሁ አግኝቷል፡፡ የምርመራው ሂደት በዚያው አቅጣጫ እንዲጓዝ አድርጎ እቅድና
ስልቱንም ቀይሶታል፡፡ ስለ አስቻለው ሁኔታ ታፈሡን በልዑንና መርዕድን ሲያነጋግር ባመሽበት ሶስተኛ ቀን ላይ ዓለሙ መርጋንና መብራቴ ባዩን ሁለቱንም በአንድ ጊዜ ከቢሮው አስቀረባቸውና «ልብ ብላችሁ አድምጡኝ» ሲል ሀምሳ አለቃ አስጠነቀቃቸው፥ ዓለሙና መብራቴ ከፊቱ ተቀምጠው የሚሆኑት ሁኔታ በራሱ ውስጣቸውን ያስነብበዋል።
«ሔዋን ተስፋዬ የምትባል ሴት ወዳጃችሁ እንደሆነች ቃል በሰጣችሁበት ወረቀት ላይ ፊርማችሁን አኑራችኋል ነው ወይስ እይደለም?» ሲል ጠየቃቸው።
👍12🔥1
«ነው! ነው!» አሉ በፍርሀት ስሜት ይቁነጠነጡ ጀመር።
ሃምሳ አለቃ አንዲት ወረቀት ከጠረጴዛው ላይ ብድግ አድርጎ እያሳያቸው ይቺ ወረቀት ግን ቅጥፈታችሁን አረጋግጣባችኋለች
ሔዋን ድንግል ስለመሆኗ
የምታረጋግጥ የሐኪም ወረቀት ናት፡፡» ብሎ ወረቀቱን ጠረጴዛ ላይ በክብር ከአስቀመጠ በኋላ እንደገና አየት እያደረጋቸው
«ዋሽታችኋል ወይስ እልዋሻችሁም» ሲል ጠየቃቸው፡፡ ዓለሙና መብራቴ እርስ በእርስ ተያዩ፡፡ ከንፈራቸውን በምላሳቸው
እያራሱ ይቅበጠበጡ ጀመር።
«ተናገሯ!»
ዓለሙ መርጋ ድንገት ብድግ አለና «እውነቱን አወጣለሁ ጌታዬ » አለ እጆቹን ወደ ኋላ አቆላልፎ እጅ እየነሳ።
«እንተስ?» አለና ሀምሳ አለቃ በመብራቴ ላይ አፈጠጠ፡፡ መብራቲም ልክ እንደ ዓለሙ ብድግ ብሎ ግልጥ አድርጌ አወጣለሁ ጌታዬ!» አለና እጅ ነሳ፡፡
ሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ከመቀመጫው ብድግ አለ፡፡ ከጠረጴዛው ላይ ሁለት ንፁህ ወረቀቶችን እያነሳ። ወደ ሀለቱም ጠጋ በማለት አንዳንድ እያደላቸው
ምን ዓይነት ውለታ ሊከፈላችሁ ቃል እንደተገባላችሁ፣ እንዲሁም በዚህ ጉዳይ ላይ የት፣ መቼና ከማን ጋር እንደተነጋገራችሁ በራሳችሁ እጅ ጽፋችሁ ታመጣላችሁ፡»ካለ በኋላ በማስጠንቀቂያ ዓይነት ሌባ ጣቱን ቀስሮ «ልብ በሉ በሁለታችሁ ጽሁፍ ላይ እንዲት ልዩነት ብትገኝ ሁለታችሁም ዕዳ ትገባላችሁ፡፡» አለና ወደ በሩ ራመድ እያለ «ኑ ተከተሉኝ:: አላቸው:: ይዟቸወ ወጣ፡፡ በፖሊስ ጣቢያው ግቢ ውስጥዐበሚገኙ ሁለት የተለያዩ ክፍሎች ውስጥ ለየብቻ አስገብቶ ቆለፈባቸው፡ በግምት አንድ ሰዓት በኋላ የተከፈተላቸው ዓለሙና መብራቴ ያቀረቡለት ፅሁፍ ለሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ
ለከሰዓት በኋላ ስራው ምቹ ሁኔታ ፈጠረለት። በዚያው መሰረት ሸዋዬንና በድሉን ከእያሉበት እየለቀመ ለዚያውም አንዱ ስለሌሳ በማያውቁበት ሁኔታ ለየብቻ እስር ቤት ከቷቸው አደረ፡፡ በነጋታው ጠዋት በቅድሚያ ዓለሙንና መብራቴን ወደ ቢሮ አስጠራና ጎን ለጎን አስቀምጦ
«ስሙ! አላቸው ተራ በተራ እየተመለከተ።
«አቤት! አቤት አሉ በየተራ፡፡»
«ከጻፋችሁት ወረቀት ለይ እንደተረዳሁት፣ ዓለሙ የመኪና ሾፌር፡ መብራቴ ደግሞ ረዳትና ገንዘብ ያዥ ሆናችሁ ልትቀጠሩ በበድሉ አሸናፊ በተገባላችሁ ቃል መሰረት በንጹህ ሰው ላይ አሳፋሪ የስም ማጥፋት ወንጀል
ፈጽማችኋል። ከእንግዲህ እናንተን ነጻ ሊያደርጋችሁ የሚችለው በዋና ጠንሳሾች ላይ ቋሚ ምስክር ሆናችሁ ስትገኙ ብቻ ነው:» አለና «አሁን ዋናዎቹን ወንጀለኞች እዚሁ አላችሁበት ላቀርባቸው ነው፡፡ እናንተም ከፊታቸው ቆማችሁ ወንጀሉን
ትፈጽሙ ዘንድ በእነሱ የተነገራችሁን ሁሉ በዝርዝር ስለመናገራቸው ቀድማችሁ
ልትገልጹላቸው ይገባል፡፡ አለና «ታደርጋላችሁ ወይስ አታደርጉትም» ሲል ቆጣ ብሎ ጠየቃቸው።
«እናደርጋለን::» አሉ ሁለቱም በአንድ ላይ
ሃምሳ እለቃው ሽዋዬና በድሉን ወዲያው አስቀረባቸው። እነሱን በአንድ በኩል አለሙና መብራቱን ደግሞ በሌላ በኩል አስቁሞ ፊት ለፊት አፋጠጣቸው ትናት በዓለሙና በመብራቴ ተጽፈው የቀረበትን ወረቀቶች በእጁ ጠልጠል አድርጎ ያዘና «አለሙና መብራቴ» ሲል ጠራችው።
«አቤት! አቤት!» አሉ በተከታታይ።
«እነዚህ ወረቀቶች እናኖተ በሔዋን ተስፋዬ ለይ እንድትፈጽሙ በበዶሉና ሸዋዬ የታቀደውን ሁሉ የዘረዘራችሁበት ናቸው።» አለና
ረዓዕተኛ ምብራቱ» ሲል«ዋሸሁ?» ሲል ጠየቃቸው።
«እውነት ነው ትክክል ነው። አሉ ዓለመዳ መብራቱ»
ሃምሳ አለቃው ወደ ሸዋዬና በድሉ ዞር ብሎ «ላታመልጡ መያዛችሁን አወቃችሁ?» ሲል ጠየቃቸው።
«ሁለቱም አንገታቸውን ደፉ፡፡»
ሃምሳ አለቃው የጠረጴዛ ደውል አቃጨለና ረዳቱ ፖሊስ ሲመጣለት ሸዋዬን ዓለሙን እና መብርሃቴን ወደ እስር ቤት አስወሰዳቸው በድሉ አሸናፊ
ብቻውን ተገኘ።
«አቶ በድሉ» ሲል ጠራው የሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ፡፡
«አቤተ!»
«ሔዋን ተስፋዬ ምን ዓይነት በደል ብትፈጽምብህ ነው የወሮ መንጋ
ያዘምትክባት?» ሲል ረጋ ብሎ ጠየቀው፡፡
«እስደብድባኛለች»
«በማን?»
«በልሁ ተገኔ በሚባል ጥጋበኛ»
«ሥነ ሥርዓት» ሲል ጮኸበት ሀምሳ አለቃ ዓይኑን አፍጥጦ እያየው ጣቱን ቀስሮ፡፡ከበልሁ ተገኔ ቡጢ ያተረፈህን አምላክ ማመስገን ትተህ ደግሞ
በህግ ቦታ ላይ ተቀምጠህ ልትዘልፈው ትሞክራለህ?» አለው እልህ እየተናነቀውና በንዴት ፊቱ ልውጥውጥ እያለ።
በድሉ ከመደንገጡ የተነሳ በዓይኑ መግቢያ ቀዳዳ የሚፈልግ ይመስል ወደ ላይ ወደ ታች፣ ወደ ቀኝ ወደ ግራ ዓይኑን እያማተረ ይቁነጥነጥ ጀመር።
«በምን ተገናኝታችሁ ነው ያስደበደበችህ?
«እወዳታለሁ!»
«ለምን ወደድከኝ ብላ አስደበደበችህ?»
«መሰለኝ::»
«ስለዚህ ልትበቀላት ፈለክ?»
«የራሷ እህት ናት የገፋፋችኝና መላውን የፈጠረችልኝ::»
«ስሟን ጥራታ!»
«ሸዋዬ::» አለና በድሉ እነዚያን ገጣጣ ጥርሶቹን የባስ ግጥጥ አደረጋቸው፡፡
ላብ ላብ ብሎት ጭንቀቱ ይታወቅበታል።.....
💫ይቀጥላል💫
ሃምሳ አለቃ አንዲት ወረቀት ከጠረጴዛው ላይ ብድግ አድርጎ እያሳያቸው ይቺ ወረቀት ግን ቅጥፈታችሁን አረጋግጣባችኋለች
ሔዋን ድንግል ስለመሆኗ
የምታረጋግጥ የሐኪም ወረቀት ናት፡፡» ብሎ ወረቀቱን ጠረጴዛ ላይ በክብር ከአስቀመጠ በኋላ እንደገና አየት እያደረጋቸው
«ዋሽታችኋል ወይስ እልዋሻችሁም» ሲል ጠየቃቸው፡፡ ዓለሙና መብራቴ እርስ በእርስ ተያዩ፡፡ ከንፈራቸውን በምላሳቸው
እያራሱ ይቅበጠበጡ ጀመር።
«ተናገሯ!»
ዓለሙ መርጋ ድንገት ብድግ አለና «እውነቱን አወጣለሁ ጌታዬ » አለ እጆቹን ወደ ኋላ አቆላልፎ እጅ እየነሳ።
«እንተስ?» አለና ሀምሳ አለቃ በመብራቴ ላይ አፈጠጠ፡፡ መብራቲም ልክ እንደ ዓለሙ ብድግ ብሎ ግልጥ አድርጌ አወጣለሁ ጌታዬ!» አለና እጅ ነሳ፡፡
ሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ ከመቀመጫው ብድግ አለ፡፡ ከጠረጴዛው ላይ ሁለት ንፁህ ወረቀቶችን እያነሳ። ወደ ሀለቱም ጠጋ በማለት አንዳንድ እያደላቸው
ምን ዓይነት ውለታ ሊከፈላችሁ ቃል እንደተገባላችሁ፣ እንዲሁም በዚህ ጉዳይ ላይ የት፣ መቼና ከማን ጋር እንደተነጋገራችሁ በራሳችሁ እጅ ጽፋችሁ ታመጣላችሁ፡»ካለ በኋላ በማስጠንቀቂያ ዓይነት ሌባ ጣቱን ቀስሮ «ልብ በሉ በሁለታችሁ ጽሁፍ ላይ እንዲት ልዩነት ብትገኝ ሁለታችሁም ዕዳ ትገባላችሁ፡፡» አለና ወደ በሩ ራመድ እያለ «ኑ ተከተሉኝ:: አላቸው:: ይዟቸወ ወጣ፡፡ በፖሊስ ጣቢያው ግቢ ውስጥዐበሚገኙ ሁለት የተለያዩ ክፍሎች ውስጥ ለየብቻ አስገብቶ ቆለፈባቸው፡ በግምት አንድ ሰዓት በኋላ የተከፈተላቸው ዓለሙና መብራቴ ያቀረቡለት ፅሁፍ ለሃምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ
ለከሰዓት በኋላ ስራው ምቹ ሁኔታ ፈጠረለት። በዚያው መሰረት ሸዋዬንና በድሉን ከእያሉበት እየለቀመ ለዚያውም አንዱ ስለሌሳ በማያውቁበት ሁኔታ ለየብቻ እስር ቤት ከቷቸው አደረ፡፡ በነጋታው ጠዋት በቅድሚያ ዓለሙንና መብራቴን ወደ ቢሮ አስጠራና ጎን ለጎን አስቀምጦ
«ስሙ! አላቸው ተራ በተራ እየተመለከተ።
«አቤት! አቤት አሉ በየተራ፡፡»
«ከጻፋችሁት ወረቀት ለይ እንደተረዳሁት፣ ዓለሙ የመኪና ሾፌር፡ መብራቴ ደግሞ ረዳትና ገንዘብ ያዥ ሆናችሁ ልትቀጠሩ በበድሉ አሸናፊ በተገባላችሁ ቃል መሰረት በንጹህ ሰው ላይ አሳፋሪ የስም ማጥፋት ወንጀል
ፈጽማችኋል። ከእንግዲህ እናንተን ነጻ ሊያደርጋችሁ የሚችለው በዋና ጠንሳሾች ላይ ቋሚ ምስክር ሆናችሁ ስትገኙ ብቻ ነው:» አለና «አሁን ዋናዎቹን ወንጀለኞች እዚሁ አላችሁበት ላቀርባቸው ነው፡፡ እናንተም ከፊታቸው ቆማችሁ ወንጀሉን
ትፈጽሙ ዘንድ በእነሱ የተነገራችሁን ሁሉ በዝርዝር ስለመናገራቸው ቀድማችሁ
ልትገልጹላቸው ይገባል፡፡ አለና «ታደርጋላችሁ ወይስ አታደርጉትም» ሲል ቆጣ ብሎ ጠየቃቸው።
«እናደርጋለን::» አሉ ሁለቱም በአንድ ላይ
ሃምሳ እለቃው ሽዋዬና በድሉን ወዲያው አስቀረባቸው። እነሱን በአንድ በኩል አለሙና መብራቱን ደግሞ በሌላ በኩል አስቁሞ ፊት ለፊት አፋጠጣቸው ትናት በዓለሙና በመብራቴ ተጽፈው የቀረበትን ወረቀቶች በእጁ ጠልጠል አድርጎ ያዘና «አለሙና መብራቴ» ሲል ጠራችው።
«አቤት! አቤት!» አሉ በተከታታይ።
«እነዚህ ወረቀቶች እናኖተ በሔዋን ተስፋዬ ለይ እንድትፈጽሙ በበዶሉና ሸዋዬ የታቀደውን ሁሉ የዘረዘራችሁበት ናቸው።» አለና
ረዓዕተኛ ምብራቱ» ሲል«ዋሸሁ?» ሲል ጠየቃቸው።
«እውነት ነው ትክክል ነው። አሉ ዓለመዳ መብራቱ»
ሃምሳ አለቃው ወደ ሸዋዬና በድሉ ዞር ብሎ «ላታመልጡ መያዛችሁን አወቃችሁ?» ሲል ጠየቃቸው።
«ሁለቱም አንገታቸውን ደፉ፡፡»
ሃምሳ አለቃው የጠረጴዛ ደውል አቃጨለና ረዳቱ ፖሊስ ሲመጣለት ሸዋዬን ዓለሙን እና መብርሃቴን ወደ እስር ቤት አስወሰዳቸው በድሉ አሸናፊ
ብቻውን ተገኘ።
«አቶ በድሉ» ሲል ጠራው የሀምሳ አለቃ መኮንን ዳርጌ፡፡
«አቤተ!»
«ሔዋን ተስፋዬ ምን ዓይነት በደል ብትፈጽምብህ ነው የወሮ መንጋ
ያዘምትክባት?» ሲል ረጋ ብሎ ጠየቀው፡፡
«እስደብድባኛለች»
«በማን?»
«በልሁ ተገኔ በሚባል ጥጋበኛ»
«ሥነ ሥርዓት» ሲል ጮኸበት ሀምሳ አለቃ ዓይኑን አፍጥጦ እያየው ጣቱን ቀስሮ፡፡ከበልሁ ተገኔ ቡጢ ያተረፈህን አምላክ ማመስገን ትተህ ደግሞ
በህግ ቦታ ላይ ተቀምጠህ ልትዘልፈው ትሞክራለህ?» አለው እልህ እየተናነቀውና በንዴት ፊቱ ልውጥውጥ እያለ።
በድሉ ከመደንገጡ የተነሳ በዓይኑ መግቢያ ቀዳዳ የሚፈልግ ይመስል ወደ ላይ ወደ ታች፣ ወደ ቀኝ ወደ ግራ ዓይኑን እያማተረ ይቁነጥነጥ ጀመር።
«በምን ተገናኝታችሁ ነው ያስደበደበችህ?
«እወዳታለሁ!»
«ለምን ወደድከኝ ብላ አስደበደበችህ?»
«መሰለኝ::»
«ስለዚህ ልትበቀላት ፈለክ?»
«የራሷ እህት ናት የገፋፋችኝና መላውን የፈጠረችልኝ::»
«ስሟን ጥራታ!»
«ሸዋዬ::» አለና በድሉ እነዚያን ገጣጣ ጥርሶቹን የባስ ግጥጥ አደረጋቸው፡፡
ላብ ላብ ብሎት ጭንቀቱ ይታወቅበታል።.....
💫ይቀጥላል💫
❤10👍7
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“መንግሥታችሁን ታጥናላችሁ፤ አልጋችሁን ትጠብቅላችሁ” እያሉ
መረቋቸው።
ሕዝቡ ከሚፈልጋቸው ነገሮች አንዱ አብያተ ክርስቲያናት
እንዲሠሩለት በመሆኑ ምንትዋብ ስለጉዳዩ ከልጇ ከብርሃን ሰገድ
ኢያሱ ጋር መከረች። ኢያሱ አስራ አንድ ዓመት አልፎታል። ንጉሠ
ነገሥቱ እሱ በመሆኑ፣ሳታማክረው የምታደርገው ነገር የለም።
አንድ ከሰዐት በኋላ፣ ቤተመንግሥት እንግዳ መቀበያው ክፍል ተቀምጠዋል። ሁለቱም ያንን መጠነኛ ስፋት ያለውን ክፍል ይወዱታል።ቅልብጭ ያለ በመሆኑ፣ የልባቸውን ለመጫወትና ስለመንግሥት ሆነ
ስለራሳቸው ጉዳይ ለማውራት ይመቻቸዋል።
ቀይ ከፋይ ጨርቅ የለበሱ ወንበሮች ዙርያውን ተደርድረዋል።
ምንትዋብ ከመግቢያው በስተቀኝ በኩል ከቀንድ የተሠራው የካባና
የባርኔጣ ማሳረፊያ ላይ ጎን ለጎን የተሰቀሉትን የእሷንና የእሱን ካባዎች ትመለከታለች። የቀረበላትን ጠጅ ቀመሰችና ቀና ብላ አየችው።
ኢያሱ ደረስህልኝ። እንዲህ አድገህ በማየቴ ታላቅ ደስታ
ይሰማኛል። ደጅ ኻልወጣሁ እያልክ ምታስቸግርበት ግዝየ ስንኳ ሩቅ አልነበረም። ያነዜ ዛዲያ አንዱ ይገድልብኛል እያልሁ እጨነቅ ነበር።አሁን እያደግህ ስትመጣ ሁሉ ነገር እየገባህ መጣ። እዝጊሃር ይመስገን” አለችው።
“አንቺ እኮ ለኔ በጣም ስለምትጨነቂ ነው እንጂ ምወጣውና ምገባው ኸሰው ጋር ነው። ምኑ ነው ሲጨንቅሽ የነበረው?”
“አየ ኢያሱ የእናት ሆድ ምን ያለ እንደሆነ አለማወቅህ ነው
እንዲህ ሚያስብልህ። አሁን እንደምታየው አገራችን ሰላም ሁኗል እኔም እንግዲህ ፊት አንስቸልህ እንደነበረው ልቤ ያለው ቤተክሲያን ማሠራት ላይ ነው። ድኻው ቤተክሲያን እንድናሠራለት ይፈልጋል ። እኔም ብሆን ነፍስ ካወቅሁ ዠምሮ ክፍሌ ለሆነችው ለቁስቋም ማርያም ቤተክሲያን ማሳነጽ ፈልጋለሁ። ጃንሆይም እኮ በነገሡ ባመታቸው ነው
ኸዝኸ ኸጐንደር ቅዱስ ሩፋኤልን የተከሉት። ደፈጫ ኪዳነ ምረትንም
እሳቸው ናቸው የደበሩ። አያትህ ታላቁ ኢያሱም ቢሆኑ ደብረብርሃን
ሥላሴንና አደባባይ ተክለሃይማኖትን የመሳሰሉ ቤተክሲያኖች ተክለዋል። ታቦት ተሸክመው እደብረብርሃን ሥላሤ ከመንበሩ ሲያገቡ ማዶል እንዴ፡-
ወዴት ሂዶ ኑራል ሰሞነኛ ቄሱ፣
ታቦት ተሸከመ ዘውዱን ትቶ ኢያሱ።
የተሸሽገውን ያባቱን ቅስና፤
ገለጠው ኢያሱ ታቦት አነሳና።
አየነው ኢያሱ ደብረብርሃን ቁሞ፣
ሰውነቱን ትቶ መላክ ሆነ ደሞ።
ሥላሴን ቢሸከም ኢያሱ ገነነ፤
ላራቱ ኪሩቤል አምስተኛ ሆነ።
ተብሎ የተገጠመላቸው?” አለችው።
ፈገግ አለ።
ጐንደር የገባች ቀን ያየቻቸውን፣ ከዚያ በኋላ የተሳለመቻቸውን፣
የደጎመቻቸውንና ሳትሰስት ጉልት እና መሬት የሰጠቻቸውን አብያት
ክርስቲያናት ሁሉ ባየችና ባሰበች ቁጥር፣ ጐንደር የቤተክርስቲያን
ባለፀጋ እንደሆነች ብታውቅም፣ የኔ የምትላትን እንደምታሠራ ስትዝት ቆየታ ጊዜው አሁን ነው pብላለች። ከባሏ ሞት በኋላ፣ “ሁሉን በግዝየው ማረግ” የሚለው ሐሳብ አእምሮዋን በመግዛቱ ጊዜ ሳታባክን ማድረግ
ያለባትን ማድረግ እንዳለባት ራሷን ስታስታውስ ቆይታለች።
እናም እንዳልሁህ ለቁስቋም ቤተክሲያን ላቆምላት ተነስቻለሁ።"
“አንቺ እናቴ እንዳልሽው ይሁን” አላት።
“ያባቶችህ በረከት አይለይህ። እኔ መቸም አሳቤ ብዙ ነው።
ቤተክሲያን ብቻ ሳይሆን ለኔም ቤተመንግሥትና ሌላም ሌላም ማሠራት ፈልጋለሁ። አንተም የራስህ መኖሪያ ያስፈልግሀል። ይኸ ላንተ ሊሆንህ ይችላል” አለችው።
አሁን የሚኖሩበት አፄ ፋሲለደስ ቅጥር ግቢ ውስጥ ስላሠራችው
ቤተመንግሥት እያወራች። ቀጥላም፣ “ሙያ ያላቸው ጠርአና ሶሪያዎቹ ኸኛ ሰዎች ጋር ሁነው ቢሠሩ ብዬ አስቤያለሁ። እንዳው እንደ ገብረሥላሤ ያለ ግንበኛ ባገኝማ! እንዳው እንዴት ያለ ግንበኛ ነበር ይላሉ። በአያትህ ግዝየ ዠምሮ ነበረ። ኸኛ ሰዎችም አላፊ ሁነው ሚሠሩም መድባለሁ።”
ባለችው ተስማማ።
ሳይውል ሳያድር ግንበኞችና ባለሙያዎች ተቀጥረው ከፋሲለደስ ቤተመንግሥት እምብዛም ሳይርቅ፣ ጉብታ ላይ የደብረ ፀሐይ ቁስቋም ግንባታ ተጀመረ። ባጭር ጊዜ መቃረቢያው ተሠርቶ አልቆ ቅዳሜ
ቀን ታቦተ ሕጉ ከአቡነ ክርስቶዶሉ ቤት ተነስቶ ወደ ቁስቋም ሲወሰድ፣የፊት ዐጀብ ከፊት እየመራ፣ የጎንና የኋላ ዐጀብ ተከትሎ፣ አስቴር ብላ የሰየመቻትን ሕፃን ከግራዝማች ኢያሱ በቅርቡ የወለደችው አራሷ ምንትዋብ በበቅሎ፣ ዳግማዊ ኢያሱ በፈረስ ሆነው፣ የወርቅ በትረ መንግሥታቸውን ጨብጠውና ግርማ ሞገስ ተጎናጽፈው፣ ለሽኝት
ወጡ።
ዐቃቤ ሰዐቱና ዕጨጌው እነሱን ሲከተሉ፣ ካህናቱ ቀይና አረንጓዴ
ለብሰው ሰንደቅ እያውለበለቡ፣ የወርቅና የብር መስቀልና የወርቅ
ፀናፅል ይዘው፣ እየዘመሩና እያሸበሸቡ፣ ነጋሪት እየተጎሰመ፣ መኳንንቱ፣ሊቃውንቱ፣ ወይዛዝርቱና ባለሟሉ ደግሞ እንደየደረጃቸው ተሰልፈው
ተከተሉ።
ሕዝቡ መንገድ ዳር ቆሞ መሬት እየሳመ በዕልልታና በሆታ
ተቀበላቸው። ታቦተ ሕጉ በአቡኑ ተባርኮ ቤተመቅደስ ገባ።
ምንትዋብም ዋናውን የቁስቋም ማርያም ሆነ የሌሎች ግንባታዎችን እንዲከታተሉ አዛዥ ተክለሃይማኖትን፣ አዛዥ ሕርያቆስን፣ አዛዥ ናቡቴን፣ አዛዥ ማሞንና በጅሮንድ ኢሳያስን የበላይ ተቆጣጣሪ አድርጋ
ሾመች። ግሪክና ሶርያውያን ሕንጻ ሥራ አዋቂዎችም ተፈልገው
መጥተው ከሃገሬው ሰው ጋር ሆነው እንዲሠሩ ተደረገ።
ምንትዋብና ኢያሱ ከሥራው አልተለዩም። ምንትዋብ ዘወትር
ጠዋት የቤተመንግሥት ጉዳይ ከፈጸመችና ካስፈጸመች በኋላ፣ እሷ በቅሎ ላይ፣ ኢያሱ ፈረስ ላይ ሆነው በባልደራስ በር ወጥተው ቁስቋም ግንባታ ስፍራ ይሄዳሉ።
ኢያሱ ከቀቢዎች ጎን ሆኖ እየቀባ፣ እሷ እየተቸች፣ ያልወደደችውን
እያስፈረሰች፣ ራሷ በምትፈልገው መሠረት እያሰራች፣ ዕንጨት
ከአርማጨሆና ከወልቃይት እያስመጣች፣ በድንጋይ ባለ ሰባት በሯ ቁስቋም ማርያም ተሠራች። ውስጥ መግቢያ ደረጃዎቿ ከሕንድ በመጣ ሸክላ ተሰሩላት። ግቢዋ ዝግባ፣ ጥድና ወይራ ተተከለበት፣ አፈር ደብረ
ቍስቋም ከምትገኝበት ሃገር ከግብፅ መጥቶ ተበተነበት። ቁስቋም ከውስጥና ከውጭ በወርቅ አሸበረቀች።
ምንትዋብ በሥዕል ልታስጌጣት ብላ ያንን የልጅነት ምስሏን የላከውን ሠዓሊ ማስመጣት ፈለገች። ትዝ ሲላት የሰውየውን ሆነ የመነኩሴውን ስም አታውቅም። መነኩሴውን ራሳቸውን ማን ብላ እንምታስፈልጋቸው ግራ ገባት፤ ተበሳጨች።
በመጨረሻም ቁስቋም ጐንደር ባሉ ሠዓሊዎች ሥራዎች አጌጠች።ምንትዋብ ከውስጥ የማርያምን ሥዕል አሥላ፣ ከፋይ ካባዋን በትንንሹ አስቀድዳ ዙርያውን አስለጠፈችበት::
ግንባታ መጠናቀቂያው ላይ ማስጌጫ ገንዘብ ሲያጥር፣ ሥራው እንዳይቋረጥ ምንትዋብ ከራሷ ወርቅ፣ ቀለበቷ ሳይቀር፣ ሰጠች።አንድ ሰሞን ጐንደር “ጉድ” አለ፤ “እቴጌ የጣታቸው ቀለበት ሳይቀር ለቤተክሲያን ማሠሪያ ሰጡ” እያለ አደነቀ።
የቁስቋም ማርያም ግንባታ በሦስት ዓመት ውስጥ ተጠናቀቀ።
ታቦቷ በታላቅ በዓል ቋሚ ማደሪያዋ ስትገባ ሕዝቡ፣ “እሰይ! እሰይ!” አለ፣ አመሰገነ። ካህናቱ ምንትዋብንና ኢያሱን፣ “
ለማርያም ቁስቋምን
እንዳቆማችሁላት፣ ቤተመቅደሷንም ዐይናችሁ እንቅልፍ ሳያይ ደፋ ቀና
ብላችሁ እንደሠራችሁላት፣ ለናንተም ትቁምላችሁ። መንግሥታችሁን ታጥናላችሁ፤ አልጋችሁን ትጠብቅላችሁ” እያሉ መረቋቸው።
ምንትዋብ ከልጇ ጋር ቁስቋም ማርያምን ማደራጀት ላይ አተኮረች። አንድ ቀን፣ የየደብሩን ካህናትና ሊቃውንት ወርቅ ሰቀላ ሰበሰበቻቸው።
“እቴጌ ምን ሊሉን ነው?” እያሉ እርስ በእርስ ተጠያየቁ።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
“መንግሥታችሁን ታጥናላችሁ፤ አልጋችሁን ትጠብቅላችሁ” እያሉ
መረቋቸው።
ሕዝቡ ከሚፈልጋቸው ነገሮች አንዱ አብያተ ክርስቲያናት
እንዲሠሩለት በመሆኑ ምንትዋብ ስለጉዳዩ ከልጇ ከብርሃን ሰገድ
ኢያሱ ጋር መከረች። ኢያሱ አስራ አንድ ዓመት አልፎታል። ንጉሠ
ነገሥቱ እሱ በመሆኑ፣ሳታማክረው የምታደርገው ነገር የለም።
አንድ ከሰዐት በኋላ፣ ቤተመንግሥት እንግዳ መቀበያው ክፍል ተቀምጠዋል። ሁለቱም ያንን መጠነኛ ስፋት ያለውን ክፍል ይወዱታል።ቅልብጭ ያለ በመሆኑ፣ የልባቸውን ለመጫወትና ስለመንግሥት ሆነ
ስለራሳቸው ጉዳይ ለማውራት ይመቻቸዋል።
ቀይ ከፋይ ጨርቅ የለበሱ ወንበሮች ዙርያውን ተደርድረዋል።
ምንትዋብ ከመግቢያው በስተቀኝ በኩል ከቀንድ የተሠራው የካባና
የባርኔጣ ማሳረፊያ ላይ ጎን ለጎን የተሰቀሉትን የእሷንና የእሱን ካባዎች ትመለከታለች። የቀረበላትን ጠጅ ቀመሰችና ቀና ብላ አየችው።
ኢያሱ ደረስህልኝ። እንዲህ አድገህ በማየቴ ታላቅ ደስታ
ይሰማኛል። ደጅ ኻልወጣሁ እያልክ ምታስቸግርበት ግዝየ ስንኳ ሩቅ አልነበረም። ያነዜ ዛዲያ አንዱ ይገድልብኛል እያልሁ እጨነቅ ነበር።አሁን እያደግህ ስትመጣ ሁሉ ነገር እየገባህ መጣ። እዝጊሃር ይመስገን” አለችው።
“አንቺ እኮ ለኔ በጣም ስለምትጨነቂ ነው እንጂ ምወጣውና ምገባው ኸሰው ጋር ነው። ምኑ ነው ሲጨንቅሽ የነበረው?”
“አየ ኢያሱ የእናት ሆድ ምን ያለ እንደሆነ አለማወቅህ ነው
እንዲህ ሚያስብልህ። አሁን እንደምታየው አገራችን ሰላም ሁኗል እኔም እንግዲህ ፊት አንስቸልህ እንደነበረው ልቤ ያለው ቤተክሲያን ማሠራት ላይ ነው። ድኻው ቤተክሲያን እንድናሠራለት ይፈልጋል ። እኔም ብሆን ነፍስ ካወቅሁ ዠምሮ ክፍሌ ለሆነችው ለቁስቋም ማርያም ቤተክሲያን ማሳነጽ ፈልጋለሁ። ጃንሆይም እኮ በነገሡ ባመታቸው ነው
ኸዝኸ ኸጐንደር ቅዱስ ሩፋኤልን የተከሉት። ደፈጫ ኪዳነ ምረትንም
እሳቸው ናቸው የደበሩ። አያትህ ታላቁ ኢያሱም ቢሆኑ ደብረብርሃን
ሥላሴንና አደባባይ ተክለሃይማኖትን የመሳሰሉ ቤተክሲያኖች ተክለዋል። ታቦት ተሸክመው እደብረብርሃን ሥላሤ ከመንበሩ ሲያገቡ ማዶል እንዴ፡-
ወዴት ሂዶ ኑራል ሰሞነኛ ቄሱ፣
ታቦት ተሸከመ ዘውዱን ትቶ ኢያሱ።
የተሸሽገውን ያባቱን ቅስና፤
ገለጠው ኢያሱ ታቦት አነሳና።
አየነው ኢያሱ ደብረብርሃን ቁሞ፣
ሰውነቱን ትቶ መላክ ሆነ ደሞ።
ሥላሴን ቢሸከም ኢያሱ ገነነ፤
ላራቱ ኪሩቤል አምስተኛ ሆነ።
ተብሎ የተገጠመላቸው?” አለችው።
ፈገግ አለ።
ጐንደር የገባች ቀን ያየቻቸውን፣ ከዚያ በኋላ የተሳለመቻቸውን፣
የደጎመቻቸውንና ሳትሰስት ጉልት እና መሬት የሰጠቻቸውን አብያት
ክርስቲያናት ሁሉ ባየችና ባሰበች ቁጥር፣ ጐንደር የቤተክርስቲያን
ባለፀጋ እንደሆነች ብታውቅም፣ የኔ የምትላትን እንደምታሠራ ስትዝት ቆየታ ጊዜው አሁን ነው pብላለች። ከባሏ ሞት በኋላ፣ “ሁሉን በግዝየው ማረግ” የሚለው ሐሳብ አእምሮዋን በመግዛቱ ጊዜ ሳታባክን ማድረግ
ያለባትን ማድረግ እንዳለባት ራሷን ስታስታውስ ቆይታለች።
እናም እንዳልሁህ ለቁስቋም ቤተክሲያን ላቆምላት ተነስቻለሁ።"
“አንቺ እናቴ እንዳልሽው ይሁን” አላት።
“ያባቶችህ በረከት አይለይህ። እኔ መቸም አሳቤ ብዙ ነው።
ቤተክሲያን ብቻ ሳይሆን ለኔም ቤተመንግሥትና ሌላም ሌላም ማሠራት ፈልጋለሁ። አንተም የራስህ መኖሪያ ያስፈልግሀል። ይኸ ላንተ ሊሆንህ ይችላል” አለችው።
አሁን የሚኖሩበት አፄ ፋሲለደስ ቅጥር ግቢ ውስጥ ስላሠራችው
ቤተመንግሥት እያወራች። ቀጥላም፣ “ሙያ ያላቸው ጠርአና ሶሪያዎቹ ኸኛ ሰዎች ጋር ሁነው ቢሠሩ ብዬ አስቤያለሁ። እንዳው እንደ ገብረሥላሤ ያለ ግንበኛ ባገኝማ! እንዳው እንዴት ያለ ግንበኛ ነበር ይላሉ። በአያትህ ግዝየ ዠምሮ ነበረ። ኸኛ ሰዎችም አላፊ ሁነው ሚሠሩም መድባለሁ።”
ባለችው ተስማማ።
ሳይውል ሳያድር ግንበኞችና ባለሙያዎች ተቀጥረው ከፋሲለደስ ቤተመንግሥት እምብዛም ሳይርቅ፣ ጉብታ ላይ የደብረ ፀሐይ ቁስቋም ግንባታ ተጀመረ። ባጭር ጊዜ መቃረቢያው ተሠርቶ አልቆ ቅዳሜ
ቀን ታቦተ ሕጉ ከአቡነ ክርስቶዶሉ ቤት ተነስቶ ወደ ቁስቋም ሲወሰድ፣የፊት ዐጀብ ከፊት እየመራ፣ የጎንና የኋላ ዐጀብ ተከትሎ፣ አስቴር ብላ የሰየመቻትን ሕፃን ከግራዝማች ኢያሱ በቅርቡ የወለደችው አራሷ ምንትዋብ በበቅሎ፣ ዳግማዊ ኢያሱ በፈረስ ሆነው፣ የወርቅ በትረ መንግሥታቸውን ጨብጠውና ግርማ ሞገስ ተጎናጽፈው፣ ለሽኝት
ወጡ።
ዐቃቤ ሰዐቱና ዕጨጌው እነሱን ሲከተሉ፣ ካህናቱ ቀይና አረንጓዴ
ለብሰው ሰንደቅ እያውለበለቡ፣ የወርቅና የብር መስቀልና የወርቅ
ፀናፅል ይዘው፣ እየዘመሩና እያሸበሸቡ፣ ነጋሪት እየተጎሰመ፣ መኳንንቱ፣ሊቃውንቱ፣ ወይዛዝርቱና ባለሟሉ ደግሞ እንደየደረጃቸው ተሰልፈው
ተከተሉ።
ሕዝቡ መንገድ ዳር ቆሞ መሬት እየሳመ በዕልልታና በሆታ
ተቀበላቸው። ታቦተ ሕጉ በአቡኑ ተባርኮ ቤተመቅደስ ገባ።
ምንትዋብም ዋናውን የቁስቋም ማርያም ሆነ የሌሎች ግንባታዎችን እንዲከታተሉ አዛዥ ተክለሃይማኖትን፣ አዛዥ ሕርያቆስን፣ አዛዥ ናቡቴን፣ አዛዥ ማሞንና በጅሮንድ ኢሳያስን የበላይ ተቆጣጣሪ አድርጋ
ሾመች። ግሪክና ሶርያውያን ሕንጻ ሥራ አዋቂዎችም ተፈልገው
መጥተው ከሃገሬው ሰው ጋር ሆነው እንዲሠሩ ተደረገ።
ምንትዋብና ኢያሱ ከሥራው አልተለዩም። ምንትዋብ ዘወትር
ጠዋት የቤተመንግሥት ጉዳይ ከፈጸመችና ካስፈጸመች በኋላ፣ እሷ በቅሎ ላይ፣ ኢያሱ ፈረስ ላይ ሆነው በባልደራስ በር ወጥተው ቁስቋም ግንባታ ስፍራ ይሄዳሉ።
ኢያሱ ከቀቢዎች ጎን ሆኖ እየቀባ፣ እሷ እየተቸች፣ ያልወደደችውን
እያስፈረሰች፣ ራሷ በምትፈልገው መሠረት እያሰራች፣ ዕንጨት
ከአርማጨሆና ከወልቃይት እያስመጣች፣ በድንጋይ ባለ ሰባት በሯ ቁስቋም ማርያም ተሠራች። ውስጥ መግቢያ ደረጃዎቿ ከሕንድ በመጣ ሸክላ ተሰሩላት። ግቢዋ ዝግባ፣ ጥድና ወይራ ተተከለበት፣ አፈር ደብረ
ቍስቋም ከምትገኝበት ሃገር ከግብፅ መጥቶ ተበተነበት። ቁስቋም ከውስጥና ከውጭ በወርቅ አሸበረቀች።
ምንትዋብ በሥዕል ልታስጌጣት ብላ ያንን የልጅነት ምስሏን የላከውን ሠዓሊ ማስመጣት ፈለገች። ትዝ ሲላት የሰውየውን ሆነ የመነኩሴውን ስም አታውቅም። መነኩሴውን ራሳቸውን ማን ብላ እንምታስፈልጋቸው ግራ ገባት፤ ተበሳጨች።
በመጨረሻም ቁስቋም ጐንደር ባሉ ሠዓሊዎች ሥራዎች አጌጠች።ምንትዋብ ከውስጥ የማርያምን ሥዕል አሥላ፣ ከፋይ ካባዋን በትንንሹ አስቀድዳ ዙርያውን አስለጠፈችበት::
ግንባታ መጠናቀቂያው ላይ ማስጌጫ ገንዘብ ሲያጥር፣ ሥራው እንዳይቋረጥ ምንትዋብ ከራሷ ወርቅ፣ ቀለበቷ ሳይቀር፣ ሰጠች።አንድ ሰሞን ጐንደር “ጉድ” አለ፤ “እቴጌ የጣታቸው ቀለበት ሳይቀር ለቤተክሲያን ማሠሪያ ሰጡ” እያለ አደነቀ።
የቁስቋም ማርያም ግንባታ በሦስት ዓመት ውስጥ ተጠናቀቀ።
ታቦቷ በታላቅ በዓል ቋሚ ማደሪያዋ ስትገባ ሕዝቡ፣ “እሰይ! እሰይ!” አለ፣ አመሰገነ። ካህናቱ ምንትዋብንና ኢያሱን፣ “
ለማርያም ቁስቋምን
እንዳቆማችሁላት፣ ቤተመቅደሷንም ዐይናችሁ እንቅልፍ ሳያይ ደፋ ቀና
ብላችሁ እንደሠራችሁላት፣ ለናንተም ትቁምላችሁ። መንግሥታችሁን ታጥናላችሁ፤ አልጋችሁን ትጠብቅላችሁ” እያሉ መረቋቸው።
ምንትዋብ ከልጇ ጋር ቁስቋም ማርያምን ማደራጀት ላይ አተኮረች። አንድ ቀን፣ የየደብሩን ካህናትና ሊቃውንት ወርቅ ሰቀላ ሰበሰበቻቸው።
“እቴጌ ምን ሊሉን ነው?” እያሉ እርስ በእርስ ተጠያየቁ።
👍10
“ዛሬ የፈለግኋችሁ...” አለቻቸው፣ “ዛሬ የፈለግኋችሁ ለደብረ ጠሐይ
ቁስቋም አስተዳዳሪ ሚሆን ብልህና አስተዋይ የሆነ፣ ባህላችንንና ወጋችንን ሚያቅ፣ አገርንና ወገንን ሚያኮራ፣ ቤተክሲያንን በወጉ ሚመራ፣ የተማረና የተመራመረ፣ ዐራቱን ጉባኤ ያጠናቀቀ ሰው
እንድትመርጡልኝ ነው።”
ካህናቱና ሊቃውንቱ እርስ በእርስ ተነጋገሩ። እሷ ከመሃላቸው ማንን
እንደሚመርጡ ለመስማት ተጠባበቀች።
“እቴጌ ለዝኸ ማዕረግ ኸሮብዓም ወዲያ ማን ሊመጣ?” ሲሉ
ተንጫጩ።
ሮብዓም ማነው?”
“ሮብዓምማ የመርጡ ለማርያም ተወላጅ የሆነው ሊቅ ነው” አሏት,
መምህር አእምሮ የተባሉት የቅኔ ሊቅ፣ ከመቀመጫቸው ተነሥተው:
“ኸዝሁ ኸጐንደር ሐዲሳትን መምህር ኤስድሮስ ዘንድ ነው የተማረ፣ብሉያትንም ኸዝሁ ያጠና። መቸም በካህናት ሆነ በሊቃውንት ዘንድ እሱን ሚያህል ዝና ማንስ አተረፈ? እቴጌ ሮብዓም ታላቅ ሊቅ ነው፣ኸሱ ወዲያ ማን ሊመጣ?”
የተሰበሰበው ካህንና ሊቅ፣ “ይበጅ! ይበጅ! ኸሱ ወዲያ ማን ሊመጣ?” አለ።
“አሁን የት ነው ያለ?” ሲል ጠየቀ፣ ኢያሱ።
“እዛው እመርጡለማርያም ነው ያለ” አሉ፣ መምህር አእምሮ።
“እንግዲያስ ባስቸኳይ ይምጣ” አለች፣ ምንትዋብ።
ስብሰባው ሲበተን ሮብዓምን ይዞ የሚመጣ ሰው ወደ መርጡለማርያም
ተላከ።በዚያው ሰሞን
ካህናቱንና ሊቃውንቱን ድጋሚ ሰበሰበች ለቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚውሉ መጻሕፍት ዝርዝር እንዲሰጧት።በዝርዝሩ መሠረት በመቶዎች የሚቆጠሩ መጻሕፍት እንዲሰበሰቡ
ተደርጎ ዕቃ ቤት ተሠርቶላቸው መጻሕፍቱ እዚያ ተቀመጡ።
በቁመናቸው ማማርና በዕውቀታቸው ጥልቀት አወዳድራ “ድምጠ መረዋ” የሆኑ መቶ ኃምሳ ካህናት፣ መቶ አስራ ሰባት የብራና ሊቃውንትና ኃምሳ ዘበኞች አስመደበች። ለቁስቋም ማርያም አገልግሎት የሚውል
ዕጨጌው፣ ዐቃቤ ሰዐቱ፣ ሊቃውንቱና ካህናቱ ባሉበት ተመዝግቦ ምንትዋብና ኢያሱ ቁጥሩ በርካታ የሆነ የቤተክርስቲያን መገልገየና
ለቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚውል መሬት ለአገልጋዮችም ጭምር ሰጡ።
ሳምንታት አልፈዋል። ሮብዓም ጐንደር ደርሶ ምንትዋብ ፊት ቀረበ።ስታየው የተባለው ሰው ዓይነት መሆኑ ገባት። ገጽታው ላይ ሊቅነቱን አየች። ዐይኖቹ የዕውቀት ብርሃን ሲረጩ፣ መላ ሰውነቱ ታማኝነቱን ለቁስቋም አስተዳዳሪነት የሰጠቻቸውን
መመዘኛዎች በሙሉ ማሟላቱን ፊቱ ላይ አነበበች። ካህናቱና
ሊቃውንቱ፣ “ከሮብዓም ወዲያ ማን ሊመጣ” ያሉት እውነት መሆኑን ሲመሰክር አስተዋለች።
አረጋገጠች።
ስታነጋግረው ከተባለውም በላይ ሆኖ አገኘችው። ቁስቋም ያለጥርጥር አስተዳዳሪ እንዳገኘች አውቃ ልቧ ተደላደለ። መልአከ ፀሐይ ብላ የደብረ ፀሐይ ቁስቋም አለቃ አድርጋ ሾመችው። የራስ ወርቅ ታሠረለት። ለክብሩም የወርቅ መስቀል፣ የወርቅ ጫማና በወርቅ ያጌጠ ካባ ተሸለመ። ለደብረ ፀሐይ ቁስቋም ለተደረገው መደራጀት ሁሉ
በካህናቱ፣ በሊቃውንቱና በሕዝቡ ዘንድ ታላቅ ደስታና ፈንጠዝያ ሆነ።
ፈንጠዝያው በደንብ ሳያልቅ ደፈረሰ። ጐንደርና ዙርያዋ ፈንጣጣ ገብቶ አስራ አምስት ዓመት እየተጠጋው ያለው ኢያሱ በበሽታው ተጠቃ፤ በጠና ታመመ። ሁለተኛ ልጇን እርጉዝ የነበረችው ምንትዋብ ይሞትብኛል ብላ ሰጋች። መሠሪ ወስዳ ከእናቷ ጋር መኝታውን የሙጥኝ ብላ አስታመመች። የማርያምን ምስል ራስጌው አስቀምጣ ጠዋት ማታ ጤንነቱ እንዲመለስለት ጸለየች።
ጐንደሬዎች ወሬውን ሲሰሙ ጭንቅ ያዛቸው።
ከጐንደር ውጭ ሳይቀር መኳንንት ሊጠይቁ መጡ። ቀስ በቀስ
ላጋው ንጉሠ ነገሥት ከተኛበት ቀና አለ። ምንትዋብና እናቷ
በእፎይታ ተነፈሱ። ቤተመንግሥት ውስጥ ታላቅ ደስታ ሆነ።
መኳንንቱ አሸርጠው እስክስታ ወረዱ። ካህናት ፈጣሪን አመሰገኑ፤ ወረቡ፤ ዘመሩ። ሊቃውንት ቅኔ ተቀኙ።
ጐንደሬዎች መንገድ ላይ ፈሰው ደስታቸውን በዘፈን፣ በዕልልታና
በጭፈራ ገለጹ።....
✨ይቀጥላል✨
ቁስቋም አስተዳዳሪ ሚሆን ብልህና አስተዋይ የሆነ፣ ባህላችንንና ወጋችንን ሚያቅ፣ አገርንና ወገንን ሚያኮራ፣ ቤተክሲያንን በወጉ ሚመራ፣ የተማረና የተመራመረ፣ ዐራቱን ጉባኤ ያጠናቀቀ ሰው
እንድትመርጡልኝ ነው።”
ካህናቱና ሊቃውንቱ እርስ በእርስ ተነጋገሩ። እሷ ከመሃላቸው ማንን
እንደሚመርጡ ለመስማት ተጠባበቀች።
“እቴጌ ለዝኸ ማዕረግ ኸሮብዓም ወዲያ ማን ሊመጣ?” ሲሉ
ተንጫጩ።
ሮብዓም ማነው?”
“ሮብዓምማ የመርጡ ለማርያም ተወላጅ የሆነው ሊቅ ነው” አሏት,
መምህር አእምሮ የተባሉት የቅኔ ሊቅ፣ ከመቀመጫቸው ተነሥተው:
“ኸዝሁ ኸጐንደር ሐዲሳትን መምህር ኤስድሮስ ዘንድ ነው የተማረ፣ብሉያትንም ኸዝሁ ያጠና። መቸም በካህናት ሆነ በሊቃውንት ዘንድ እሱን ሚያህል ዝና ማንስ አተረፈ? እቴጌ ሮብዓም ታላቅ ሊቅ ነው፣ኸሱ ወዲያ ማን ሊመጣ?”
የተሰበሰበው ካህንና ሊቅ፣ “ይበጅ! ይበጅ! ኸሱ ወዲያ ማን ሊመጣ?” አለ።
“አሁን የት ነው ያለ?” ሲል ጠየቀ፣ ኢያሱ።
“እዛው እመርጡለማርያም ነው ያለ” አሉ፣ መምህር አእምሮ።
“እንግዲያስ ባስቸኳይ ይምጣ” አለች፣ ምንትዋብ።
ስብሰባው ሲበተን ሮብዓምን ይዞ የሚመጣ ሰው ወደ መርጡለማርያም
ተላከ።በዚያው ሰሞን
ካህናቱንና ሊቃውንቱን ድጋሚ ሰበሰበች ለቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚውሉ መጻሕፍት ዝርዝር እንዲሰጧት።በዝርዝሩ መሠረት በመቶዎች የሚቆጠሩ መጻሕፍት እንዲሰበሰቡ
ተደርጎ ዕቃ ቤት ተሠርቶላቸው መጻሕፍቱ እዚያ ተቀመጡ።
በቁመናቸው ማማርና በዕውቀታቸው ጥልቀት አወዳድራ “ድምጠ መረዋ” የሆኑ መቶ ኃምሳ ካህናት፣ መቶ አስራ ሰባት የብራና ሊቃውንትና ኃምሳ ዘበኞች አስመደበች። ለቁስቋም ማርያም አገልግሎት የሚውል
ዕጨጌው፣ ዐቃቤ ሰዐቱ፣ ሊቃውንቱና ካህናቱ ባሉበት ተመዝግቦ ምንትዋብና ኢያሱ ቁጥሩ በርካታ የሆነ የቤተክርስቲያን መገልገየና
ለቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚውል መሬት ለአገልጋዮችም ጭምር ሰጡ።
ሳምንታት አልፈዋል። ሮብዓም ጐንደር ደርሶ ምንትዋብ ፊት ቀረበ።ስታየው የተባለው ሰው ዓይነት መሆኑ ገባት። ገጽታው ላይ ሊቅነቱን አየች። ዐይኖቹ የዕውቀት ብርሃን ሲረጩ፣ መላ ሰውነቱ ታማኝነቱን ለቁስቋም አስተዳዳሪነት የሰጠቻቸውን
መመዘኛዎች በሙሉ ማሟላቱን ፊቱ ላይ አነበበች። ካህናቱና
ሊቃውንቱ፣ “ከሮብዓም ወዲያ ማን ሊመጣ” ያሉት እውነት መሆኑን ሲመሰክር አስተዋለች።
አረጋገጠች።
ስታነጋግረው ከተባለውም በላይ ሆኖ አገኘችው። ቁስቋም ያለጥርጥር አስተዳዳሪ እንዳገኘች አውቃ ልቧ ተደላደለ። መልአከ ፀሐይ ብላ የደብረ ፀሐይ ቁስቋም አለቃ አድርጋ ሾመችው። የራስ ወርቅ ታሠረለት። ለክብሩም የወርቅ መስቀል፣ የወርቅ ጫማና በወርቅ ያጌጠ ካባ ተሸለመ። ለደብረ ፀሐይ ቁስቋም ለተደረገው መደራጀት ሁሉ
በካህናቱ፣ በሊቃውንቱና በሕዝቡ ዘንድ ታላቅ ደስታና ፈንጠዝያ ሆነ።
ፈንጠዝያው በደንብ ሳያልቅ ደፈረሰ። ጐንደርና ዙርያዋ ፈንጣጣ ገብቶ አስራ አምስት ዓመት እየተጠጋው ያለው ኢያሱ በበሽታው ተጠቃ፤ በጠና ታመመ። ሁለተኛ ልጇን እርጉዝ የነበረችው ምንትዋብ ይሞትብኛል ብላ ሰጋች። መሠሪ ወስዳ ከእናቷ ጋር መኝታውን የሙጥኝ ብላ አስታመመች። የማርያምን ምስል ራስጌው አስቀምጣ ጠዋት ማታ ጤንነቱ እንዲመለስለት ጸለየች።
ጐንደሬዎች ወሬውን ሲሰሙ ጭንቅ ያዛቸው።
ከጐንደር ውጭ ሳይቀር መኳንንት ሊጠይቁ መጡ። ቀስ በቀስ
ላጋው ንጉሠ ነገሥት ከተኛበት ቀና አለ። ምንትዋብና እናቷ
በእፎይታ ተነፈሱ። ቤተመንግሥት ውስጥ ታላቅ ደስታ ሆነ።
መኳንንቱ አሸርጠው እስክስታ ወረዱ። ካህናት ፈጣሪን አመሰገኑ፤ ወረቡ፤ ዘመሩ። ሊቃውንት ቅኔ ተቀኙ።
ጐንደሬዎች መንገድ ላይ ፈሰው ደስታቸውን በዘፈን፣ በዕልልታና
በጭፈራ ገለጹ።....
✨ይቀጥላል✨
👍17
#ቅፅበትና_ቅፅፈት
“ጠብ” ይላል ዝናቡ
“ጧ” ይላል መሬቱ
“ድም” ይላል ነጋሪት
“ግው” ይላል ብረቱ
“ቋ” ይላል መዘውር
“ቲክ” ይላል ሰዓቱ
እቱ እቱ እቱ
ያንቺ ፍቅር ነበር
እንደ አዲስ ሚወልደኝ
ዋዛ አያውቅም ጊዜ
“መሽቶብሃል” ብሎ
ጠምዝዞ አጎበጠኝ!
(ይሄ ሁሉ ሆኖ
ከምፅኣት በፊት ከቦታው ስትደርሺ
እኔ ያንቺ ድኩም
ጎብጨ አልቀረሁም ሬሳዬን አንሺ)
🔘ሰለሞን ሳህለ🔘
“ጠብ” ይላል ዝናቡ
“ጧ” ይላል መሬቱ
“ድም” ይላል ነጋሪት
“ግው” ይላል ብረቱ
“ቋ” ይላል መዘውር
“ቲክ” ይላል ሰዓቱ
እቱ እቱ እቱ
ያንቺ ፍቅር ነበር
እንደ አዲስ ሚወልደኝ
ዋዛ አያውቅም ጊዜ
“መሽቶብሃል” ብሎ
ጠምዝዞ አጎበጠኝ!
(ይሄ ሁሉ ሆኖ
ከምፅኣት በፊት ከቦታው ስትደርሺ
እኔ ያንቺ ድኩም
ጎብጨ አልቀረሁም ሬሳዬን አንሺ)
🔘ሰለሞን ሳህለ🔘
👍7
#ሳገኝሽ_የሚሆነው
ትናንት...
እንደ ከሰረ ሰው
ወዘናዬ ጠፍቶ ጭው ብዬ ነጣሁ
በደበኞች ደባ
አንገቴን ደፍቼ ግፍ እንደ ውሃ ጠጣሁ
ዝም ብዬ ተቀጣሁ..
ጮክ ብዬ ተቆጣሁ...
ልክ አንቺን ሳገኝሽ
ከሲኦል ሆድ ወጣሁ
ዛሬ...
የዛሬውን ትርጉም የዛሬውን ፍቺ
እንዲህ ነሽ ይልሻል ተቀበይው እንቺ
ውስብስብ ቋጠሮን ስቀሽ የምትፈቺ
ቀና እምታደርጊ ቀና ሰው ነሽ አንቺ
ምንም እንዳይገርምሽ!!!
🔘ሰለሞን ሳህለ🔘
ትናንት...
እንደ ከሰረ ሰው
ወዘናዬ ጠፍቶ ጭው ብዬ ነጣሁ
በደበኞች ደባ
አንገቴን ደፍቼ ግፍ እንደ ውሃ ጠጣሁ
ዝም ብዬ ተቀጣሁ..
ጮክ ብዬ ተቆጣሁ...
ልክ አንቺን ሳገኝሽ
ከሲኦል ሆድ ወጣሁ
ዛሬ...
የዛሬውን ትርጉም የዛሬውን ፍቺ
እንዲህ ነሽ ይልሻል ተቀበይው እንቺ
ውስብስብ ቋጠሮን ስቀሽ የምትፈቺ
ቀና እምታደርጊ ቀና ሰው ነሽ አንቺ
ምንም እንዳይገርምሽ!!!
🔘ሰለሞን ሳህለ🔘
❤6👍5😁1
#አንድ_ሌላ_መንገድ
ገደል ዋሻ ጥቁር እሳት
ተንኮል ክፋት ምቀኝነት
ሸር ደባ ሀጣ ብኩን
በግራ ጎን በቀኝ ጎን
ሕልም ራዕይ አዲስ ሕይወት
ትግል ስኬት ጣፋጭ ስሜት
ረዥም መንገድ ከፊት ለፊት
ትእዛዝ ቁጣ መርገምት ሥራይ
ያ'ዳም ቅርሻት ክፉ ክፋይ
ከላይ
እሾህ ጉድፍ አሜኬላ
ከኋላ
የድካም ድግ ጎታችና ተጎታች
ከታች
.
.
.
አንድ ተአምር ተፈጥሮ
ሕይወት መጋረጃ ቢኖራት
የሚጋረደውን ጋርጄ
ፊት ለፊት ነበረ የማያት።
🔘ሰለሞን ሳህለ🔘
ገደል ዋሻ ጥቁር እሳት
ተንኮል ክፋት ምቀኝነት
ሸር ደባ ሀጣ ብኩን
በግራ ጎን በቀኝ ጎን
ሕልም ራዕይ አዲስ ሕይወት
ትግል ስኬት ጣፋጭ ስሜት
ረዥም መንገድ ከፊት ለፊት
ትእዛዝ ቁጣ መርገምት ሥራይ
ያ'ዳም ቅርሻት ክፉ ክፋይ
ከላይ
እሾህ ጉድፍ አሜኬላ
ከኋላ
የድካም ድግ ጎታችና ተጎታች
ከታች
.
.
.
አንድ ተአምር ተፈጥሮ
ሕይወት መጋረጃ ቢኖራት
የሚጋረደውን ጋርጄ
ፊት ለፊት ነበረ የማያት።
🔘ሰለሞን ሳህለ🔘
❤8👍4
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንትዋብ አልጣሽ የተባለችውን ሁለተኛ ልጇን ወልዳ ከአራስ ቤት እንደወጣች እንደገና በግዛት ዘመኗ ልትፈጽማቸው ያሰበቻቸው ነገሮች ላይ ትኩረት አደረገች።
ትምህርት ቁስቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ ለማስጀመር ከብርሃን ሰገድ ኢያሱ ጋር መከረች። ብዙ ጊዜ እንደሚያደርጉት አንድ ቀን እንግዳ መቀበያው ክፍል ተቀምጠዋል።
ትክ ብላ አየችው። ፈንጣጣ ፊቱ ላይ ምንም ምልክት ሳይተው
ማለፉ ገረማት። በቁስቋም ረድኤት መዳኒቱ ሠርቷል። ይኸን የመሰለ መልኩን ሊያበላሽብኝ እሷ የቁስቋሟ ማረችልኝ፡፡ አሁን ኢያሱን የመሰለ ልዥ አለ? የተባረኩ እያለች በሐሳብ ጭልጥ ብላ ሄደች።
ኢያሱ በሐሳብ እንደነጎደች ኣውቆ ከሄደችበት እስክትመለስ ዐይን
ዐይኗን እያየ ጠበቃት።
“አያትህ ታላቁ ኢያሱ ለትምርት ብዙ ዋጋ ሚሰጡ ሰው ነበሩ…
አለችው፣ ከሄደችበት ስትመለስ።
“አውቃለሁ። አንቺም ነገርሽ ሁላ እንደሳቸው ነው። ደሞስ የሳቸው
ስም መቸ ኻፍሽ ጠፍቶ ያውቃል?”
ከት ብላ ስትስቅ እሱም ሳቀ።
“ስለ ትምርት ላወራህ ፈልጌ ነው የሳቸውን ስም ያነሳሁ” አለችው፣
ፈገግ ብላ። “በሳቸው ዘመን የተማሮች ቁጥር ኸዝኸ ኸደብረሥላሤ ስንኳ ብዙ ነበር ይላሉ። ስንክሳርም በብዛት የተጣፈው በሳቸው ግዝየ
ነው። እንደ ክፍለ ዮሐንስ የመሰሉ ሊቃውንትም ኸጎዣም ያመጡ
እሳቸው ናቸው። ሊቁ አዛዥ ከናፍሮም ቢሆኑ በሳቸው ግዝየ ነው የነበሩ። ዛዲያ ልነግርህ የፈለግሁት ቁስቋም ውስጥ ትምርት ቤት ማቆም ብቻ ሳይሆን፣ ለተማሮቹና ላስተማሮቹ ድጋፍ ማረግ አለብን
ሚለውን ነው።”
“እኔም ስለሱ ነግርሻለሁ እያልሁ ነበር። ሌላ ደሞ ባለፈው መጻሕፍት ኻረብኛና ኸዕብራይስጥ ወደ ግዕዝ እንዲመለሱ ፈልጋለሁ ስትይ
ማልነበር?”
"ትርጉም.... አዎ ስል ነበር። ሁሉ ባግባቡ ነው። ባለፈው መላከ
ጠሐይ ሮብዓምን ትርጉም ላይ ቢበረታ ብያቸው ኻረብኛና ኸዕብራይስጥ ወደ ግዕዝ ሚመልሱ ሰዎች አምጥተው ሥራ እንዲዠምሩ ተደርጓል።
ለእነመላከ ጠሐይ ሃይማኖትን ሚያስተምረውንና ላገር ሚጠቅመውን ሁሉ እንዲያስተረጉሙ ነግሬያቸው እነሱ ተመካክረው ወስነዋል።”
"የትርጉም ሥራ ለገዳማቱ ቢሰጥ ጥሩ ነው ሲሉ ሰምቸ።”
“ዛዲያ ምን አለ... ይሰጣል ። በጎ አሳብ ነው። ትዛዝ ሰጣለሁ። እኔ
መቸም ቢሞላልኝ አገር ሁሉ መጻፍ በመጻፍ እንዲሆንና ትምርት
እንዲስፋፋ ነው ምፈልግ። እኔ ራሴም ብሆን አንድ ቀን ስለ እመቤታችን ማርያም ታምር አስጥፋለሁ ብየ አስባለሁ። ደሞ እሑድ እሑድ ለሊቃውንቱና ለካህናቱ ግብር እናግባላቸው። አንተም ለነሱ ትልቅ ክብር አለህ። ቅኔም ተምረሀል። ቅኔ እውቀቴ እንዳንተ ባይሆንም፣ሊቃውንቱ ቅኔ ሲቀኙ ስሰማ መንፈሴ ሁሉ ይታደሳል። በተለይማ
የአክስትህን ልዥ እመት ወለተብርሃንን ስሰማ እንዳው እንደሳቸው ቅኔ በቻልሁ እላለሁ፡፡ አንተማ ኸኔም የበለጠ ትወዳቸዋለህ።”
የአክስቱ ልጅ ነገር ሲነሳ ፈገግ አለ። “ውነትሽ ነው እመት ወለተብርሃን ታላቅ የቅኔ ሊቅ ናቸው። እሑድ እሑድ ግብር ለሊቃውንቱና ለካህናቱ ማግባት ያልሽው ተገቢ ነው። በተነጋገርነው መሠረትም በአካባቢው ወይን እንዲተከል ቦታ ብታስጠኚ። ቃሮዳ አየሩ ለወይን ተስማሚ ነው ሲሉ ሰምቻለሁ። ቅርብም ነው።”
“ውነትህ ነው። ዛሬውኑ ሰው ይላካል።”
ሁለቱም ዝም አሉ።
“ግና ካህናቱና ሊቃውንቱ... ምናለ ልብሳቸውን ቢያጠዱ?” አላት።
ያልጠበቀችው በመሆኑ ከት ብላ ሳቀች። “ልብሳቸውን እንዲያጥቡ
ማረግ ይቻላል ። በጐንደር ዙርያና በየገዳማቱ እንዶድ ኣስተክለን
ልብሳቸውን እንዲያጥቡ እናረጋለና” አለችው፣ አሁንም እየሳቀች።
“ዋናዎቹ ካህናት ደሞ የወርቅ ጫማ እንዲያረጉ ፈልጋለሁ።”
“ወርቅ አሳብ ነው። ይታዘዝላቸዋል። የአክብሮትህ ምልክት ነው።
እንደገና ዝም ብለው ተቀመጡ። ኢያሱ ሐሳብ የገባው ይመስላል።
እሷም ዝም ብላ ታየዋለች።
ዐይን ዐይኗን እያየ፣ “አደን ብኸድ ትፈቅጅልኛለሽ?” እናቱን ፈሪና
አክባሪ ነው።
ዕጢዋ ዱብ አለ። አፏ ተያዘ። ሊመጣበት የሚችለው አደጋ
አሳሰባት። ጥያቄው ግን አንድ ቀን እንደሚመጣ ታውቃለች።
“ኣባትህ ስንኳ በኸዱ ቁጥር እጨነቅ ነበር። ኢያሱ እንድትኸድ
አልፈልግም፤ ጭንቀቱን አልችለውም።”
“ምን ችግር አለው?”
“ባትኸድ መርጣለሁ። ኢያሱ አልጋውን እኮ ባየነቁራኛ ሚጠባበቅአለ!”
“ሁሉስ እያደኑ ማዶል እንዴ የኖሩት?”
“ገና ልዥ እኮ ነህ ኢያሱ።”
ድምጽዋ ተርበተበተ።
“አትጨነቂ። ምንም ሚመጣ ነገር የለም። ሰዎች ይዠ ነው ምኸደው
በዝኸ ላይ ደሞ አልቆይም።”
“ኻንተ መለየት አልፈቅድም ኢያሱ ... መቸ ትነሳለህ?”
ነገ።”
“ነገ?”
“አዎ! ነገ።”
“ታሰብህበት ቆይተሀል ማለት ነዋ! መቸስ ምን ኣረጋለሁ። ቁስቋም
ደሕና ትመልስህ። በጠሎቴ አልለይህም።”
አይዞሽ አትጨነቂ። በጠዋት ስለምኸድ ካሁኑ ልሰናበትሽ” አላት፣ጠዋት መጥቶ ቢሰናበታት እንባዋን ማየት ስለማይችል። ተነስታ ወደ እልፍኟ ስትሄድ በጭንቀት ተመለከታት።
በማግስቱ ጠዋት ከእናቷ ጋር በመስኮት ቆመው የአደን ዕቃው
በቅሎ ላይ ሲጫን አይተው ሆዳቸው ባባ። ኢያሱ ፈረሱ ቀርቦለት፡ በሹሩባው ዙርያ ነጭ ሻሽ አስሮ፣ ካባውን ደርቦ ከዐጀቡ ጋር ብቅ ሲል፣ የቤተመንግሥት ባለሟሉ፣ ወታደሩ፣ ጋሻ ጃግሬውና ሌላው ሰገደ።ምንትዋብና እናቷ ግን ሲቃ ያዛቸው።
ከቤተመንግሥት ግቢ ሲወጣ፣
ምንትዋብ ጩሂ ጩሂ አላት። እንኰዬ ትከሻዋን መታ መታ አደረጓት።እሳቸውም እንባ እንባ ብሏቸዋል፤ ግን እሷን ማረጋጋት መረጡ።
ሁለቱም በየክፍላቸው ገብተው ወገባቸውን በገመድ አስረው ሱባዔ ገቡ። መሬት ላይ ተኙ። ከጥቂት ቀናት በኋላ ጸሎታቸው ሠምሮ ኢያሱ በሰላም ተመለሰ። እናትና ልጅ ገመድ ትጥቃቸውን ፈቱ።የነበሩበትን ጭንቀት ሳይናገሩ በደስታ ተቀበሉት።
እያደር የአደን ፍቅር በረታበት፤ መዝናኛው አደረገው። በሄደ ቁጥር
እናቱና አያቱ ወገባቸውን በገመድ ጠፍረው መሬት መተኛትና ሱባዔ
መግባት፣ ሲመጣ ደግሞ ገመዳቸውን ፈትተው መጣል፣ ጸማቸውን መፍታት ልማድ አደረጉት። እንደዚህ እያለም ኢያሱ የከፋ ነገር ሳይገጥመው ቀለል ያለ አደን ማካሄዱን ቀጠለ።
ከእናቱ ጋር በተስማሙት መሠረት ከንባብ ቤት እስከ ትርጓሜ ቤት
ደብረ ፀሐይ ቁስቋም ማርያምን በትምህርት ለማደራጀት ወጡ ወረዱ።ሁለት መቶ የሚጠጉ ምርጥ ሊቃውንት ከጐንደር ገዳማትና ከሌላ የሃገሪቱ ክፍሎች እየመጡ ወንበር ዘረጉ
የተማሪ ጎጆዎች ተቀለሱ። ትምህርት ከቁስቋም ሌላ በየገዳማቱና በየደብሮቹ ተስፋፋ። ወሬውን የሰማ ተማሪ ከየቦታው ፈልሶ ጐንደር ገባ፡፡ ጐንደር ከመቼውም ጊዜ የበለጠ የሊቃውንት ማፍሪያና
መሰብሰቢያ ሆነች። ከጐንደር ውጭም ትምህርት ቤቶች ተስፋፉ።
የዜማ ሊቃውንት ድርጎ በማግኘታቸው ሙያቸውን አበለፀጉ ቤተክርስቲያንን አገለገሉ፤ ቤተመንግሥትንም አዝናኑ።
የሥዕል ሥራ በአያሌው አደገ። ቀለም አጠቃቀም ጥንት ከነበረው
ለውጥ አመጣ፣ የአቀራረብና የይዘት ለውጦች መጡ። ሠዓሊዎች ድጎማ እየተደረገላቸው አብያተ ክርስቲያናትን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ አስጌጡ።
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንትዋብ አልጣሽ የተባለችውን ሁለተኛ ልጇን ወልዳ ከአራስ ቤት እንደወጣች እንደገና በግዛት ዘመኗ ልትፈጽማቸው ያሰበቻቸው ነገሮች ላይ ትኩረት አደረገች።
ትምህርት ቁስቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ ለማስጀመር ከብርሃን ሰገድ ኢያሱ ጋር መከረች። ብዙ ጊዜ እንደሚያደርጉት አንድ ቀን እንግዳ መቀበያው ክፍል ተቀምጠዋል።
ትክ ብላ አየችው። ፈንጣጣ ፊቱ ላይ ምንም ምልክት ሳይተው
ማለፉ ገረማት። በቁስቋም ረድኤት መዳኒቱ ሠርቷል። ይኸን የመሰለ መልኩን ሊያበላሽብኝ እሷ የቁስቋሟ ማረችልኝ፡፡ አሁን ኢያሱን የመሰለ ልዥ አለ? የተባረኩ እያለች በሐሳብ ጭልጥ ብላ ሄደች።
ኢያሱ በሐሳብ እንደነጎደች ኣውቆ ከሄደችበት እስክትመለስ ዐይን
ዐይኗን እያየ ጠበቃት።
“አያትህ ታላቁ ኢያሱ ለትምርት ብዙ ዋጋ ሚሰጡ ሰው ነበሩ…
አለችው፣ ከሄደችበት ስትመለስ።
“አውቃለሁ። አንቺም ነገርሽ ሁላ እንደሳቸው ነው። ደሞስ የሳቸው
ስም መቸ ኻፍሽ ጠፍቶ ያውቃል?”
ከት ብላ ስትስቅ እሱም ሳቀ።
“ስለ ትምርት ላወራህ ፈልጌ ነው የሳቸውን ስም ያነሳሁ” አለችው፣
ፈገግ ብላ። “በሳቸው ዘመን የተማሮች ቁጥር ኸዝኸ ኸደብረሥላሤ ስንኳ ብዙ ነበር ይላሉ። ስንክሳርም በብዛት የተጣፈው በሳቸው ግዝየ
ነው። እንደ ክፍለ ዮሐንስ የመሰሉ ሊቃውንትም ኸጎዣም ያመጡ
እሳቸው ናቸው። ሊቁ አዛዥ ከናፍሮም ቢሆኑ በሳቸው ግዝየ ነው የነበሩ። ዛዲያ ልነግርህ የፈለግሁት ቁስቋም ውስጥ ትምርት ቤት ማቆም ብቻ ሳይሆን፣ ለተማሮቹና ላስተማሮቹ ድጋፍ ማረግ አለብን
ሚለውን ነው።”
“እኔም ስለሱ ነግርሻለሁ እያልሁ ነበር። ሌላ ደሞ ባለፈው መጻሕፍት ኻረብኛና ኸዕብራይስጥ ወደ ግዕዝ እንዲመለሱ ፈልጋለሁ ስትይ
ማልነበር?”
"ትርጉም.... አዎ ስል ነበር። ሁሉ ባግባቡ ነው። ባለፈው መላከ
ጠሐይ ሮብዓምን ትርጉም ላይ ቢበረታ ብያቸው ኻረብኛና ኸዕብራይስጥ ወደ ግዕዝ ሚመልሱ ሰዎች አምጥተው ሥራ እንዲዠምሩ ተደርጓል።
ለእነመላከ ጠሐይ ሃይማኖትን ሚያስተምረውንና ላገር ሚጠቅመውን ሁሉ እንዲያስተረጉሙ ነግሬያቸው እነሱ ተመካክረው ወስነዋል።”
"የትርጉም ሥራ ለገዳማቱ ቢሰጥ ጥሩ ነው ሲሉ ሰምቸ።”
“ዛዲያ ምን አለ... ይሰጣል ። በጎ አሳብ ነው። ትዛዝ ሰጣለሁ። እኔ
መቸም ቢሞላልኝ አገር ሁሉ መጻፍ በመጻፍ እንዲሆንና ትምርት
እንዲስፋፋ ነው ምፈልግ። እኔ ራሴም ብሆን አንድ ቀን ስለ እመቤታችን ማርያም ታምር አስጥፋለሁ ብየ አስባለሁ። ደሞ እሑድ እሑድ ለሊቃውንቱና ለካህናቱ ግብር እናግባላቸው። አንተም ለነሱ ትልቅ ክብር አለህ። ቅኔም ተምረሀል። ቅኔ እውቀቴ እንዳንተ ባይሆንም፣ሊቃውንቱ ቅኔ ሲቀኙ ስሰማ መንፈሴ ሁሉ ይታደሳል። በተለይማ
የአክስትህን ልዥ እመት ወለተብርሃንን ስሰማ እንዳው እንደሳቸው ቅኔ በቻልሁ እላለሁ፡፡ አንተማ ኸኔም የበለጠ ትወዳቸዋለህ።”
የአክስቱ ልጅ ነገር ሲነሳ ፈገግ አለ። “ውነትሽ ነው እመት ወለተብርሃን ታላቅ የቅኔ ሊቅ ናቸው። እሑድ እሑድ ግብር ለሊቃውንቱና ለካህናቱ ማግባት ያልሽው ተገቢ ነው። በተነጋገርነው መሠረትም በአካባቢው ወይን እንዲተከል ቦታ ብታስጠኚ። ቃሮዳ አየሩ ለወይን ተስማሚ ነው ሲሉ ሰምቻለሁ። ቅርብም ነው።”
“ውነትህ ነው። ዛሬውኑ ሰው ይላካል።”
ሁለቱም ዝም አሉ።
“ግና ካህናቱና ሊቃውንቱ... ምናለ ልብሳቸውን ቢያጠዱ?” አላት።
ያልጠበቀችው በመሆኑ ከት ብላ ሳቀች። “ልብሳቸውን እንዲያጥቡ
ማረግ ይቻላል ። በጐንደር ዙርያና በየገዳማቱ እንዶድ ኣስተክለን
ልብሳቸውን እንዲያጥቡ እናረጋለና” አለችው፣ አሁንም እየሳቀች።
“ዋናዎቹ ካህናት ደሞ የወርቅ ጫማ እንዲያረጉ ፈልጋለሁ።”
“ወርቅ አሳብ ነው። ይታዘዝላቸዋል። የአክብሮትህ ምልክት ነው።
እንደገና ዝም ብለው ተቀመጡ። ኢያሱ ሐሳብ የገባው ይመስላል።
እሷም ዝም ብላ ታየዋለች።
ዐይን ዐይኗን እያየ፣ “አደን ብኸድ ትፈቅጅልኛለሽ?” እናቱን ፈሪና
አክባሪ ነው።
ዕጢዋ ዱብ አለ። አፏ ተያዘ። ሊመጣበት የሚችለው አደጋ
አሳሰባት። ጥያቄው ግን አንድ ቀን እንደሚመጣ ታውቃለች።
“ኣባትህ ስንኳ በኸዱ ቁጥር እጨነቅ ነበር። ኢያሱ እንድትኸድ
አልፈልግም፤ ጭንቀቱን አልችለውም።”
“ምን ችግር አለው?”
“ባትኸድ መርጣለሁ። ኢያሱ አልጋውን እኮ ባየነቁራኛ ሚጠባበቅአለ!”
“ሁሉስ እያደኑ ማዶል እንዴ የኖሩት?”
“ገና ልዥ እኮ ነህ ኢያሱ።”
ድምጽዋ ተርበተበተ።
“አትጨነቂ። ምንም ሚመጣ ነገር የለም። ሰዎች ይዠ ነው ምኸደው
በዝኸ ላይ ደሞ አልቆይም።”
“ኻንተ መለየት አልፈቅድም ኢያሱ ... መቸ ትነሳለህ?”
ነገ።”
“ነገ?”
“አዎ! ነገ።”
“ታሰብህበት ቆይተሀል ማለት ነዋ! መቸስ ምን ኣረጋለሁ። ቁስቋም
ደሕና ትመልስህ። በጠሎቴ አልለይህም።”
አይዞሽ አትጨነቂ። በጠዋት ስለምኸድ ካሁኑ ልሰናበትሽ” አላት፣ጠዋት መጥቶ ቢሰናበታት እንባዋን ማየት ስለማይችል። ተነስታ ወደ እልፍኟ ስትሄድ በጭንቀት ተመለከታት።
በማግስቱ ጠዋት ከእናቷ ጋር በመስኮት ቆመው የአደን ዕቃው
በቅሎ ላይ ሲጫን አይተው ሆዳቸው ባባ። ኢያሱ ፈረሱ ቀርቦለት፡ በሹሩባው ዙርያ ነጭ ሻሽ አስሮ፣ ካባውን ደርቦ ከዐጀቡ ጋር ብቅ ሲል፣ የቤተመንግሥት ባለሟሉ፣ ወታደሩ፣ ጋሻ ጃግሬውና ሌላው ሰገደ።ምንትዋብና እናቷ ግን ሲቃ ያዛቸው።
ከቤተመንግሥት ግቢ ሲወጣ፣
ምንትዋብ ጩሂ ጩሂ አላት። እንኰዬ ትከሻዋን መታ መታ አደረጓት።እሳቸውም እንባ እንባ ብሏቸዋል፤ ግን እሷን ማረጋጋት መረጡ።
ሁለቱም በየክፍላቸው ገብተው ወገባቸውን በገመድ አስረው ሱባዔ ገቡ። መሬት ላይ ተኙ። ከጥቂት ቀናት በኋላ ጸሎታቸው ሠምሮ ኢያሱ በሰላም ተመለሰ። እናትና ልጅ ገመድ ትጥቃቸውን ፈቱ።የነበሩበትን ጭንቀት ሳይናገሩ በደስታ ተቀበሉት።
እያደር የአደን ፍቅር በረታበት፤ መዝናኛው አደረገው። በሄደ ቁጥር
እናቱና አያቱ ወገባቸውን በገመድ ጠፍረው መሬት መተኛትና ሱባዔ
መግባት፣ ሲመጣ ደግሞ ገመዳቸውን ፈትተው መጣል፣ ጸማቸውን መፍታት ልማድ አደረጉት። እንደዚህ እያለም ኢያሱ የከፋ ነገር ሳይገጥመው ቀለል ያለ አደን ማካሄዱን ቀጠለ።
ከእናቱ ጋር በተስማሙት መሠረት ከንባብ ቤት እስከ ትርጓሜ ቤት
ደብረ ፀሐይ ቁስቋም ማርያምን በትምህርት ለማደራጀት ወጡ ወረዱ።ሁለት መቶ የሚጠጉ ምርጥ ሊቃውንት ከጐንደር ገዳማትና ከሌላ የሃገሪቱ ክፍሎች እየመጡ ወንበር ዘረጉ
የተማሪ ጎጆዎች ተቀለሱ። ትምህርት ከቁስቋም ሌላ በየገዳማቱና በየደብሮቹ ተስፋፋ። ወሬውን የሰማ ተማሪ ከየቦታው ፈልሶ ጐንደር ገባ፡፡ ጐንደር ከመቼውም ጊዜ የበለጠ የሊቃውንት ማፍሪያና
መሰብሰቢያ ሆነች። ከጐንደር ውጭም ትምህርት ቤቶች ተስፋፉ።
የዜማ ሊቃውንት ድርጎ በማግኘታቸው ሙያቸውን አበለፀጉ ቤተክርስቲያንን አገለገሉ፤ ቤተመንግሥትንም አዝናኑ።
የሥዕል ሥራ በአያሌው አደገ። ቀለም አጠቃቀም ጥንት ከነበረው
ለውጥ አመጣ፣ የአቀራረብና የይዘት ለውጦች መጡ። ሠዓሊዎች ድጎማ እየተደረገላቸው አብያተ ክርስቲያናትን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ አስጌጡ።
👍9