#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...ጃን ተከል ከወትሮው የበለጠ ሰው ተሰብስቦበታል። ወሬው ሁሉ ስለ ቅዳሜው ግብርና ስለ ምንትዋብ ውበት ነው። ቅዳሜ ዕለት ኣብርሃ ቤተመንግሥት በር ላይ የድኃ ተራ እስኪደርስ ጠብቆ ግብር ተካፍሎ ነበርና በአኮፋዳው
ከየዓይነቱ ምግብ ጠቅጥቆ መጥቶ ጥላዬን እንዲበላ
ሲጋብዘው አልበላም ብሎታል።
አብርሃ ምንትዋብን ባያያትም፣
ስለግብሩ ትልቅነት ሲያወራ አልበቃው በማለቱ ጥላዬ ደከመኝ ልተኛ ብሎት ተለያይተዋል።
ጥላዬ፣ ዋርካው ጠርዝ ላይ ቆሞ፣ “ምንትዋብ ብለው ስም አወጡላት እያሉ ወሬውን ሲቀባበሉ ሰማ። አብርሃን ሲያየው ካንዱ ወደ ሌላው እየሄደ ወሬ ይጨልፋል። ምነው እንደሱ የማላውቃት ባረገኝ። ወደ
ቅጥር ውጭ እኔ ዛፉ ስር ቁሜ አንቺ ነጠላ ተከናንበሽ ገና ኸደጀሰላሙ የልቤን ሳላወጋሽ። የቅርብ ሩቅ ሁኜ ስላንቺ ሰማለሁ። ኸዛ ኸበተክሲያን ወለቴ ምንትዋብ አሉሽ ለኔ ሁሌም ወለቴ ነሽ፡፡ አንድ ቀን ስንኳ ብቅ ስትይ ልቤ ሚተረከከውን ምን ግዝየም አልረሳው። አንድ ቀን ያነን ድንቅ ፊትሽን እሥል ይሆናል። እስተዛው የወፍታው ኻንቺ ጋር ይሁን ብሎ የፍቅራቸውን ምዕራፍ መዝጋት እንዳለበት ለልቡ አስገነዘበ።
አብርሃ የቃረመውን ወሬ ሊነግረው ሲመጣ፣ ጥላዬ መስማት አልፈለገም። “ኸዛው እንኸድና ለሥላሤ ምስጋናዬን ላቅርብ” አለው፣ ወሬውን ሳይጀምር።
“ምናለ፣ እንኸዳ” አለው፣ ግራ የተጋባው አብርሃ።አብርሃ ወደቤቱ ሲሄድ ጥላዬ ቤተክርስቲያኑ ደጅ ላይ ተደፍቶ ምስጋናውን አቀረበ። የተሰበረ ልቡን ሥላሤ እንዲጠግኑለትም ጸሎት
አድርጎ ከዐይኑ ያመለጠውን እንባ ሰው ሳያየው በጋቢው ጠራርጎ ተነሣ።ከመጣ ጊዜ ጀምሮ ሲቀመጥበት የነበረው ዋንዛ ዛፍ ሥር ተቀምጦአካባቢውን ሲቃኝ፣ የቆሎ ተማሪው ግማሹ የለቀመውን ዕንጨት በእቅፉ
ይዞ ወደቤቱ ይሄዳል፣ ሌላው ውሃ ቀድቶ መመለሱ ነው። በየአጥሩ ጥግ መነኮሳትና አረጋውያን ተቀምጠው ዳዊት ይደግማሉ፣ የቁም ጸሐፊው ብራና ላይ ይጽፋል፣ አንዱ ብራና ሲደጉስ ሌላው ቅዱሳት መጻሕፍትን
ያስጌጣል።
ጥላዬ፣ ለሥራቸው በሚሰጡት ትኩረት ተገረመ። እሱም እንደነሱ
ተቀምጦ ሥራውን የሚሠራበትን ቀን ናፈቀ። አለቃ ሔኖክ ትምህርት
እስኪያስጀምሩት ቸኮለ። እዚያው ግቢውን ሲቃኝ ቆይቶ፣ ከሰዐት
በኋላ፣ ወደ እሳቸው ቤት አመራ።
እሳቸው ስላልነበሩ ደጅ ተቀመጠ። ወርቄ በር ላይ ቆማ የሆነ
ያልሆነውን ስትጠይቀውና ሲመልስ ቆይተው፣ ወደ ውስጥ እንደገባች አለቃ ሔኖክ ቅጥር ግቢው ገቡ።
“አምሽተህ ነው?” ብለውት ወደ ውስጥ ገቡ።ቆየት ብለው ወጥተው ወደ ጓሮ እንዲመጣ በእጃቸው አመለከቱት ኩታውን እያስተካከለ ተከተላቸው። ጎጆውጋ ሲደርሱ፣ “ይህቻት
እንግዲህ ማደሪያህ” አሉት።
"እመቤቴ ትስጥልኝ” አላቸው፣ ለጥ ብሎ እጅ ነሥቶ።
አንገቱን ወደ ውስጥ መዘዝ አድርጎ ተመለከተ። ከአንድ አነስተኛ ቁርበት በስተቀር ጎጆዋ ውስጥ ሌላ ምንም ነገር የለም። የአቧራዋ ሽታ ይሰነፍጣል ።
“እዝች ሁነህ ሥራህን ትሠራለህ። የትምርት ግዝየ ሲደርስ እኔ አለሁ።ምግብ ወርቄ ትሰጥኻለች። አንተ ዛዲያ እንጨት ትለቅምላታለህ፣ ውሃ
ትቀዳላታለህ፣ ልብስም ታጥባለህ” አሉት።
“እረ ምን ገዶኝ!”
አለቃ ወደ ቤት ሲመለሱ፣ ቁርበቱ ላይ ጋደም እንዳለ መላ አካላቱ
በሐሳብ ደክሞ ነበርና እንቅልፍ ወሰደው። ምሽት ላይ፣ ወርቄ እራቱን ይዛለት መጣች። ራቱን በልቶ ተኛ።በነጋታው አለቃ ሔኖክ በወርቄ አስጠርተውት ሲገባ እሳቸው መደብ ላይ ተቀምጠዋል። ሰላምታ ሰጥቷቸው በእሳቸው ትይዩ ተቀመጠ።
ወርቄ ቁርስ አቅርባላቸው ከበሉ በኋላ፣ አለቃ ሔኖክ፣ አነስተኛ ብራናና የቀለም ቀንድ ይዘው አብሯቸው ደጅ እንዲወጣ ነገሩት።
“ብራናና ቀለም እኔ ሰጥኻለሁ። ወደፊት ብራና ሆነ ቀለም ራስህ
ታዘጋጃለህ። ቀለም አቀማመም አሳይሀለሁ። ንድፍም አሳይህና በዚያ መሠረት ኸርኩሳኑ መኻል ምትፈልገውን ሠርተህ ታመጣልኛለኸ አሉት።
እጅ ነሥቶ ትኩረቱን እጃቸው ላይ ያለው ብራና ላይ አደረገ።
ቀስ ብለው ንድፍ እንዴት እንደሚሠራና ቀለም እንዴት እንደሚቀባ አሳዩት።
“ለነገሩ ንድፍ አይቸግርህም። በአክርማ ስትሠራ ቆይተህ የለ?”
አሉት፣ እየሳቁ።
ዐይኑን ከብራናውና ንድፉን ከሚሠሩበት የቀርከሀ ስንጥር ላይ
ሳያነሳ በአዎንታ ራሱን ነቀነቀ።
ትምህርቱን ጨርሰው እሳቸው ወደ ውስጥ ሲገቡ፣ እሱ ወደ ቤቱ
ሄደ። ጋቢውን ቁርበቱ ላይ ወርውሮ ደጅ ድንጋይ ላይ ተቀምጦ፣ለመጀመሪያ ጊዜ ሲመኝ የኖረው ብራና እጁ በመግባቱ ሊስመው ቃጣው።
ሕይወቱ ዐዲስ ምዕራፍ የያዘ መሰለው።ሥዕሉን በምን እንደሚጀምር አወጣ አወረደ... እባብ? ሳጥናኤል? ቁራ? በመጨረሻም ስለምን ሳጥናኤኔልን አልሰራም አለ፣ ለራሱ።አለቃ ሔኖክ ባሳዩት መሠረት ንድፍ ሞከረ፤ ተንጋደደበት። ብራናውን
ያበላሽ ስለመሰለው ደነገጠ። ሆኖም መሣሉን ቀጠለ። አለቅጥ ረጀም፣ግራና ቀኝ አስፈሪ ቀንዶች ያለው፣ ጆሮዎቹ በጣም ትልልቅና ጭራ ያለው ፍጡር ሣለ። ቤቱ ደጃፍ ላይ ተቀምጦ፣ ብራናውን ደጋግሞ እየተመለከተ ስቆ እንደማያውቀው ሳቀ። በነጋታው ፈራ ተባ እያለ አለቃ ሔኖክጋ ሲሄድ ወርቄ፣ “ኣፍህን እንድትሽር ልጠራህ ስል መጣህ” አለችው።
“ለመብልማ እስትትጠራ አትጠብቅ። ቤትህ እኮ ነው” አሉት፣ አለቃ ሔኖክ።
ቁርስ አድርገው ከጨረሱ በኋላ፣ “እስቲ ምን ሠራህ?” አሉት።
ብራናውን ብድግ ብሎ ሲያቀብላቸው፣ ቀረብ፣ ራቅ አድርገው ተመለከቱትና ሳቁ። “ሳጥናኤል... ማለፊያ ነው። ንድፉም መልካም ነው። ተሰጥኦ እንዳለህ ያስታውቃል” አሉት።
“ንድፉ ተንጋደደብኝ እንጂ።”
ርኩሳንን ከሀዲያንን፣ አጋንንትንና ክፉዎችን ስትሥል ንድፉ ቢንጋደድ ምንም አዶለም። ባሕሪያቸው ነው፤ መንጋደድ ይስማማቸዋል። ላንተ ግን ዋናው እጅ ማፍታታትህ ነው። ወደፊት ቅዱሳንን፣ መላዕክትንና ሌሎችን ስትሥል ግን ንድፍ ማንሻሽፍ
አይፈቀድም። በል በርታ” ብለው ብራናውን መልሰው ሰጡት።
እጅ ነሥቶ ወጣ።
በሚቀጥሉት ቀናት፣ እሳቸው በነገሩት መሠረት ጥቁር ቀለም ከተለያዩ ዕጽዋት ቀምሞ ሥዕል መሣሉን ተያያዘው። እንደሱ ቢሆን፣ ርኩሳንን ብቻ ሳይሆን የፈለገውን ቢሰራ በመረጠ። ብዙውን ጊዜ የምንትዋብ
መልክ ፊቱ ላይ ድቅን ይላል። እንደበፊቱ እንስሳውን ቤቶቹን ሁሉ
መሣል ይፈልጋል። አንዳንዴ የፈለገውን የሚሥልበት የቤታቸው ጓሮ ይናፍቀዋል።
ሥዕል በማይሥልበት፣ ለወርቄ ውሃ በማይቀዳበት፣ ዕንጨት
በማይለቅምበትና የአለቃ ሔኖክን ልብስ በማያጥብበት ጊዜ፣ ከአብርሃ ጋር ጃን ተከል እየሄደ ወሬ ይሰማል። ጃን ተከል ብቅ ማለት እሱስ ሆኖበታል። ቤተመንግሥት ግብር ሲጣል፣ አብርሃ ምግብ ብቻ ሳይሆን
ስለ ምንትዋብ ወሬ ይዞለት ይመጣል ።
፡
በትምህርቱ እየጎበዘ ሲመጣ፣ አለቃ ሔኖክ በሥራው ቢደሰቱም፣
“መልካም ነው፣ በርታ” ከማለት በስተቀር ብዙ ስለማያብራሩ ጥቂት ቅር ይሰኛል፣ ቢያሞጋግሱት ይመርጣል። የሠራውን ሲመለከቱ፣ ፊታቸው
ላይ የሚንፀባረቀውን አድናቆት ለምን በቃላት እንደማይገልጹለት
ይገርመዋል።
አንድ ቀን አስደሰቱት። ግቢው ውስጥ ተቀምጠዋል። እንዴትና
የት እንደዋለ ከጠየቁት በኋላ፣ “ጥላዬ፣ ሥዕል ኸዠመርህ ወራት
አልፈውሀል። እጅህም ጥሩ ተፍታቷል። እንደነገርሁህ ጥቂት ቆይተህ ቄሶችን፣ መሪጌታዎችን፣ ሊቀጠበብቶችን ቤተክስቲያን አካባቢ ያሉ ሰዎችን መሣል ትዝምራለህ” አሉት።
ደስ ተሰኘ።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...ጃን ተከል ከወትሮው የበለጠ ሰው ተሰብስቦበታል። ወሬው ሁሉ ስለ ቅዳሜው ግብርና ስለ ምንትዋብ ውበት ነው። ቅዳሜ ዕለት ኣብርሃ ቤተመንግሥት በር ላይ የድኃ ተራ እስኪደርስ ጠብቆ ግብር ተካፍሎ ነበርና በአኮፋዳው
ከየዓይነቱ ምግብ ጠቅጥቆ መጥቶ ጥላዬን እንዲበላ
ሲጋብዘው አልበላም ብሎታል።
አብርሃ ምንትዋብን ባያያትም፣
ስለግብሩ ትልቅነት ሲያወራ አልበቃው በማለቱ ጥላዬ ደከመኝ ልተኛ ብሎት ተለያይተዋል።
ጥላዬ፣ ዋርካው ጠርዝ ላይ ቆሞ፣ “ምንትዋብ ብለው ስም አወጡላት እያሉ ወሬውን ሲቀባበሉ ሰማ። አብርሃን ሲያየው ካንዱ ወደ ሌላው እየሄደ ወሬ ይጨልፋል። ምነው እንደሱ የማላውቃት ባረገኝ። ወደ
ቅጥር ውጭ እኔ ዛፉ ስር ቁሜ አንቺ ነጠላ ተከናንበሽ ገና ኸደጀሰላሙ የልቤን ሳላወጋሽ። የቅርብ ሩቅ ሁኜ ስላንቺ ሰማለሁ። ኸዛ ኸበተክሲያን ወለቴ ምንትዋብ አሉሽ ለኔ ሁሌም ወለቴ ነሽ፡፡ አንድ ቀን ስንኳ ብቅ ስትይ ልቤ ሚተረከከውን ምን ግዝየም አልረሳው። አንድ ቀን ያነን ድንቅ ፊትሽን እሥል ይሆናል። እስተዛው የወፍታው ኻንቺ ጋር ይሁን ብሎ የፍቅራቸውን ምዕራፍ መዝጋት እንዳለበት ለልቡ አስገነዘበ።
አብርሃ የቃረመውን ወሬ ሊነግረው ሲመጣ፣ ጥላዬ መስማት አልፈለገም። “ኸዛው እንኸድና ለሥላሤ ምስጋናዬን ላቅርብ” አለው፣ ወሬውን ሳይጀምር።
“ምናለ፣ እንኸዳ” አለው፣ ግራ የተጋባው አብርሃ።አብርሃ ወደቤቱ ሲሄድ ጥላዬ ቤተክርስቲያኑ ደጅ ላይ ተደፍቶ ምስጋናውን አቀረበ። የተሰበረ ልቡን ሥላሤ እንዲጠግኑለትም ጸሎት
አድርጎ ከዐይኑ ያመለጠውን እንባ ሰው ሳያየው በጋቢው ጠራርጎ ተነሣ።ከመጣ ጊዜ ጀምሮ ሲቀመጥበት የነበረው ዋንዛ ዛፍ ሥር ተቀምጦአካባቢውን ሲቃኝ፣ የቆሎ ተማሪው ግማሹ የለቀመውን ዕንጨት በእቅፉ
ይዞ ወደቤቱ ይሄዳል፣ ሌላው ውሃ ቀድቶ መመለሱ ነው። በየአጥሩ ጥግ መነኮሳትና አረጋውያን ተቀምጠው ዳዊት ይደግማሉ፣ የቁም ጸሐፊው ብራና ላይ ይጽፋል፣ አንዱ ብራና ሲደጉስ ሌላው ቅዱሳት መጻሕፍትን
ያስጌጣል።
ጥላዬ፣ ለሥራቸው በሚሰጡት ትኩረት ተገረመ። እሱም እንደነሱ
ተቀምጦ ሥራውን የሚሠራበትን ቀን ናፈቀ። አለቃ ሔኖክ ትምህርት
እስኪያስጀምሩት ቸኮለ። እዚያው ግቢውን ሲቃኝ ቆይቶ፣ ከሰዐት
በኋላ፣ ወደ እሳቸው ቤት አመራ።
እሳቸው ስላልነበሩ ደጅ ተቀመጠ። ወርቄ በር ላይ ቆማ የሆነ
ያልሆነውን ስትጠይቀውና ሲመልስ ቆይተው፣ ወደ ውስጥ እንደገባች አለቃ ሔኖክ ቅጥር ግቢው ገቡ።
“አምሽተህ ነው?” ብለውት ወደ ውስጥ ገቡ።ቆየት ብለው ወጥተው ወደ ጓሮ እንዲመጣ በእጃቸው አመለከቱት ኩታውን እያስተካከለ ተከተላቸው። ጎጆውጋ ሲደርሱ፣ “ይህቻት
እንግዲህ ማደሪያህ” አሉት።
"እመቤቴ ትስጥልኝ” አላቸው፣ ለጥ ብሎ እጅ ነሥቶ።
አንገቱን ወደ ውስጥ መዘዝ አድርጎ ተመለከተ። ከአንድ አነስተኛ ቁርበት በስተቀር ጎጆዋ ውስጥ ሌላ ምንም ነገር የለም። የአቧራዋ ሽታ ይሰነፍጣል ።
“እዝች ሁነህ ሥራህን ትሠራለህ። የትምርት ግዝየ ሲደርስ እኔ አለሁ።ምግብ ወርቄ ትሰጥኻለች። አንተ ዛዲያ እንጨት ትለቅምላታለህ፣ ውሃ
ትቀዳላታለህ፣ ልብስም ታጥባለህ” አሉት።
“እረ ምን ገዶኝ!”
አለቃ ወደ ቤት ሲመለሱ፣ ቁርበቱ ላይ ጋደም እንዳለ መላ አካላቱ
በሐሳብ ደክሞ ነበርና እንቅልፍ ወሰደው። ምሽት ላይ፣ ወርቄ እራቱን ይዛለት መጣች። ራቱን በልቶ ተኛ።በነጋታው አለቃ ሔኖክ በወርቄ አስጠርተውት ሲገባ እሳቸው መደብ ላይ ተቀምጠዋል። ሰላምታ ሰጥቷቸው በእሳቸው ትይዩ ተቀመጠ።
ወርቄ ቁርስ አቅርባላቸው ከበሉ በኋላ፣ አለቃ ሔኖክ፣ አነስተኛ ብራናና የቀለም ቀንድ ይዘው አብሯቸው ደጅ እንዲወጣ ነገሩት።
“ብራናና ቀለም እኔ ሰጥኻለሁ። ወደፊት ብራና ሆነ ቀለም ራስህ
ታዘጋጃለህ። ቀለም አቀማመም አሳይሀለሁ። ንድፍም አሳይህና በዚያ መሠረት ኸርኩሳኑ መኻል ምትፈልገውን ሠርተህ ታመጣልኛለኸ አሉት።
እጅ ነሥቶ ትኩረቱን እጃቸው ላይ ያለው ብራና ላይ አደረገ።
ቀስ ብለው ንድፍ እንዴት እንደሚሠራና ቀለም እንዴት እንደሚቀባ አሳዩት።
“ለነገሩ ንድፍ አይቸግርህም። በአክርማ ስትሠራ ቆይተህ የለ?”
አሉት፣ እየሳቁ።
ዐይኑን ከብራናውና ንድፉን ከሚሠሩበት የቀርከሀ ስንጥር ላይ
ሳያነሳ በአዎንታ ራሱን ነቀነቀ።
ትምህርቱን ጨርሰው እሳቸው ወደ ውስጥ ሲገቡ፣ እሱ ወደ ቤቱ
ሄደ። ጋቢውን ቁርበቱ ላይ ወርውሮ ደጅ ድንጋይ ላይ ተቀምጦ፣ለመጀመሪያ ጊዜ ሲመኝ የኖረው ብራና እጁ በመግባቱ ሊስመው ቃጣው።
ሕይወቱ ዐዲስ ምዕራፍ የያዘ መሰለው።ሥዕሉን በምን እንደሚጀምር አወጣ አወረደ... እባብ? ሳጥናኤል? ቁራ? በመጨረሻም ስለምን ሳጥናኤኔልን አልሰራም አለ፣ ለራሱ።አለቃ ሔኖክ ባሳዩት መሠረት ንድፍ ሞከረ፤ ተንጋደደበት። ብራናውን
ያበላሽ ስለመሰለው ደነገጠ። ሆኖም መሣሉን ቀጠለ። አለቅጥ ረጀም፣ግራና ቀኝ አስፈሪ ቀንዶች ያለው፣ ጆሮዎቹ በጣም ትልልቅና ጭራ ያለው ፍጡር ሣለ። ቤቱ ደጃፍ ላይ ተቀምጦ፣ ብራናውን ደጋግሞ እየተመለከተ ስቆ እንደማያውቀው ሳቀ። በነጋታው ፈራ ተባ እያለ አለቃ ሔኖክጋ ሲሄድ ወርቄ፣ “ኣፍህን እንድትሽር ልጠራህ ስል መጣህ” አለችው።
“ለመብልማ እስትትጠራ አትጠብቅ። ቤትህ እኮ ነው” አሉት፣ አለቃ ሔኖክ።
ቁርስ አድርገው ከጨረሱ በኋላ፣ “እስቲ ምን ሠራህ?” አሉት።
ብራናውን ብድግ ብሎ ሲያቀብላቸው፣ ቀረብ፣ ራቅ አድርገው ተመለከቱትና ሳቁ። “ሳጥናኤል... ማለፊያ ነው። ንድፉም መልካም ነው። ተሰጥኦ እንዳለህ ያስታውቃል” አሉት።
“ንድፉ ተንጋደደብኝ እንጂ።”
ርኩሳንን ከሀዲያንን፣ አጋንንትንና ክፉዎችን ስትሥል ንድፉ ቢንጋደድ ምንም አዶለም። ባሕሪያቸው ነው፤ መንጋደድ ይስማማቸዋል። ላንተ ግን ዋናው እጅ ማፍታታትህ ነው። ወደፊት ቅዱሳንን፣ መላዕክትንና ሌሎችን ስትሥል ግን ንድፍ ማንሻሽፍ
አይፈቀድም። በል በርታ” ብለው ብራናውን መልሰው ሰጡት።
እጅ ነሥቶ ወጣ።
በሚቀጥሉት ቀናት፣ እሳቸው በነገሩት መሠረት ጥቁር ቀለም ከተለያዩ ዕጽዋት ቀምሞ ሥዕል መሣሉን ተያያዘው። እንደሱ ቢሆን፣ ርኩሳንን ብቻ ሳይሆን የፈለገውን ቢሰራ በመረጠ። ብዙውን ጊዜ የምንትዋብ
መልክ ፊቱ ላይ ድቅን ይላል። እንደበፊቱ እንስሳውን ቤቶቹን ሁሉ
መሣል ይፈልጋል። አንዳንዴ የፈለገውን የሚሥልበት የቤታቸው ጓሮ ይናፍቀዋል።
ሥዕል በማይሥልበት፣ ለወርቄ ውሃ በማይቀዳበት፣ ዕንጨት
በማይለቅምበትና የአለቃ ሔኖክን ልብስ በማያጥብበት ጊዜ፣ ከአብርሃ ጋር ጃን ተከል እየሄደ ወሬ ይሰማል። ጃን ተከል ብቅ ማለት እሱስ ሆኖበታል። ቤተመንግሥት ግብር ሲጣል፣ አብርሃ ምግብ ብቻ ሳይሆን
ስለ ምንትዋብ ወሬ ይዞለት ይመጣል ።
፡
በትምህርቱ እየጎበዘ ሲመጣ፣ አለቃ ሔኖክ በሥራው ቢደሰቱም፣
“መልካም ነው፣ በርታ” ከማለት በስተቀር ብዙ ስለማያብራሩ ጥቂት ቅር ይሰኛል፣ ቢያሞጋግሱት ይመርጣል። የሠራውን ሲመለከቱ፣ ፊታቸው
ላይ የሚንፀባረቀውን አድናቆት ለምን በቃላት እንደማይገልጹለት
ይገርመዋል።
አንድ ቀን አስደሰቱት። ግቢው ውስጥ ተቀምጠዋል። እንዴትና
የት እንደዋለ ከጠየቁት በኋላ፣ “ጥላዬ፣ ሥዕል ኸዠመርህ ወራት
አልፈውሀል። እጅህም ጥሩ ተፍታቷል። እንደነገርሁህ ጥቂት ቆይተህ ቄሶችን፣ መሪጌታዎችን፣ ሊቀጠበብቶችን ቤተክስቲያን አካባቢ ያሉ ሰዎችን መሣል ትዝምራለህ” አሉት።
ደስ ተሰኘ።
👍15😱1
“በርታ እንግዲህ። እስታሁን ጥሩ እየሠራህ ነው። ወደፊት ደሞ
የበለጠ እየተፈተንህ ትኸዳለህ።”
ማንን እንደሚሥል ሲያስብ ከረመ።.....
፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡
በእነዚያ ወራት፣ “እቴጌ አርግዘዋል መሰል ጠዋት ጠዋት ወደላይ
ይላቸዋል” የሚል ወሬ ቤተመንግሥቱን አልፎ ጃን ተከል ሲመጣ እሱምጋ ደረሰ። የምንትዋብ እርግዝና የሁሉ ጉዳይ በመሆኑ ተገረመ።
አንድ ቀን፣ ጃን ተከል ከምንጊዜውም የበለጠ ተጣቧል። እሱና አብርሃ ገና መድረሳቸው ነው። ሰዉ በቡድን በቡድን ሆኖ ይወያያል፣ ይከራከራል፣ ይሟገታል። ጥላዬ አንዱጋ ተጠግቶ ሲያዳምጥ ወሬው ዛሬም ስለምንትዋብ እርግዝና ነው፡፡
“እቴጌይቱ ወንድ ኻልወለዱ ንጉሡ እንዴት አርገው ነው አልጋ
ወራሽ ሚያገኙ?”
ፊት የወለዷትም ሴት ናት አለ።”
“እቴጌም ሴት ኸወለዱ ጉድ ነው በለኛ!”
“ኸጉድም ጉድ ነው እንጂ።”
ጥላዬ አላስቻለውም። ጣልቃ ገባና፣ “ኸምኑ ላይ ነው ጉዱ?” አለ።
“ኧረገኝ ምን ያለ ዥል ነው በሉ? የተዣዣለ። ሴት መንገሥ
እንደማትችል አያውቅም ሁኖ ነው? አይበለውና እቴጌ ሴት ቢወልዱ እንዴት ሁኖ ነው ንጉሡ አልጋ ወራሽ ሚኖራቸው? በል እስቲ ንገረኝ?”
ጥላዬ፣ ሊቀጥለው የማይችልበት ሙግት ሆነበትና ዝም አለ።
አብርሃን በዐይኑ ፈልጎ ሲያገኘው አብርሃ የአንገቱ ስሮች እስኪገታተሩ ድረስ ከሁለት ሰዎች ጋር ይከራከራል። ጥቂት ጠብቆት ወደቤቱ ሄደ።
ቤት ሲደርስ፣ አለቃ ሔኖክ ከሰዐት በኋላ እንደሚያደርጉት ጥላ ስር
ተቀምጠው ቀለም ይቀምማሉ። አጠገባቸው ሄዶ ተቀመጠ።
“የት ቆይተህ ነው?” አሉት
“ከአብርሃ ጋር ጃን ተከል ወርደን የሰዉ ክርክር ለብቻው
አላቸው።
“ስለምን ነው ሚከራከሩ?”
“ስለ እቴጌ...” ምንትዋብ ይበላት ወለቴ ቸገረው። ገና ምንትዋብ
የሚለውን ስም አልተለማመደውም። “እቴጌዋ አርግዘዋልና ወንድ በሆነ
እያለ ሰዉ ይነታረካል።”
“መቸም ውነት ነው። ለእቴጌም ሆነ ለንጉሡ ወንድ መሆኑ ይጠቅማል።በዝኸ ግዝየ እቴጌስ ቢሆኑ ተኝተው ያድሩ መሰለህ? ቤተመንግሥት ውስጥ ያለ ወሬ ስንኳ አያስተኛቸውም። ወንድ ቢሆንላቸው ንጉሡን የሳቸው ደጋፊ የሆኑትን መኳንንት ጭምር ያስደስታሉ። እሳቸውም
ልባቸው ያርፋል።”
“ፈርዶባቸዋላ!”
“እዝጊሃር ይርዳቸው። በዝኸ ላይ ኸቋራ ናቸው።”
“ኸቋራ ቢሆኑ ምን ሞገድ አለው?”
“አየ ጥላዬ! አለው እንጂ። በአንድ በኩል መኳንንቱ የቋራ ደም
ያለው አልጋው ላይ እንዲወጣ አይፈልጉም። ቋራ እንደ ጐንደር
ማዶል። ባላገር ነው ብለው ያስባሉ። በሌላ በኩል ደሞ እወህኒ አምባ ስንቱ የነጋሢ ዘር መሰለህ አሰፍስፎ ሚወለደው ወንድ ይሁን ሴት ሚጠባበቀው። ወንድ ኸተወለደ የመንገሥ ዕድላችን ይዘገይብናል
አለያም ያመልጠናል ብለው ይሰጋሉ። ሴት የሆነች እንደሁ እነሱም ይደሰታሉ፣ ከንጉሡ ጋር ጠብ ያላቸው መኳንንትም የልባቸው ይደርሳል። ንጉሡም ቢሆኑ ዳግም ሴት ኸተወለደችላቸው ያዝናሉ።
አየህ ነገሥታቱ አልጋቸውን አሳልፈው መስጠት ስለማይፈልጉ ወንድ ልዥ ለማግኘት ሲሉ ዕቁባት ይይዛሉ። አሁን አጤ ቴዎፍሎስ...
የታላቁ ኢያሱ ወንድም፣ የጃንሆይ አጎት መሆናቸው ነው... ከሕግ
ባለቤታቸው ኸእቴጌ ወለተጽዮን ጠንተው ሲኖሩ እቴጌዋ መካን ነበሩና አልጋ ሚወርስ ልዥ አልነበራቸውም። ስለዝኸ የነጋሲ ዘር የሌላቸው የአጤ ቴዎፍሎስ እንደራሴ የነበሩት ዮስጦስ ነገሡ። አሁንም ጃንሆይ ቢሞቱ ስንኳ አልጋቸውን ሚወርስ ልዥ የለም። ለዝኸ ነው ያ ሁሉ ክርክር።”
“እቴጌ ሴት ኸወለዱ ጉድ ነው ቢሉ ጉዱ ምኑ ላይ ነው ብል አንዱ ዥል የተዣዣለ ብሎ ሰደበኝ” አላቸው፣ እየሳቀ።
አለቃ ሔኖክ እንባቸው ጠብ እስኪል ሳቁና፣ “እንግዲህ ለእቴጌ
እንጸልይላቸዋለን” አሉት።
ኧረ አጥብቄ ጸልይላታለሁ አለ፣ ለራሱ።......
✨ይቀጥላል✨
የበለጠ እየተፈተንህ ትኸዳለህ።”
ማንን እንደሚሥል ሲያስብ ከረመ።.....
፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡
በእነዚያ ወራት፣ “እቴጌ አርግዘዋል መሰል ጠዋት ጠዋት ወደላይ
ይላቸዋል” የሚል ወሬ ቤተመንግሥቱን አልፎ ጃን ተከል ሲመጣ እሱምጋ ደረሰ። የምንትዋብ እርግዝና የሁሉ ጉዳይ በመሆኑ ተገረመ።
አንድ ቀን፣ ጃን ተከል ከምንጊዜውም የበለጠ ተጣቧል። እሱና አብርሃ ገና መድረሳቸው ነው። ሰዉ በቡድን በቡድን ሆኖ ይወያያል፣ ይከራከራል፣ ይሟገታል። ጥላዬ አንዱጋ ተጠግቶ ሲያዳምጥ ወሬው ዛሬም ስለምንትዋብ እርግዝና ነው፡፡
“እቴጌይቱ ወንድ ኻልወለዱ ንጉሡ እንዴት አርገው ነው አልጋ
ወራሽ ሚያገኙ?”
ፊት የወለዷትም ሴት ናት አለ።”
“እቴጌም ሴት ኸወለዱ ጉድ ነው በለኛ!”
“ኸጉድም ጉድ ነው እንጂ።”
ጥላዬ አላስቻለውም። ጣልቃ ገባና፣ “ኸምኑ ላይ ነው ጉዱ?” አለ።
“ኧረገኝ ምን ያለ ዥል ነው በሉ? የተዣዣለ። ሴት መንገሥ
እንደማትችል አያውቅም ሁኖ ነው? አይበለውና እቴጌ ሴት ቢወልዱ እንዴት ሁኖ ነው ንጉሡ አልጋ ወራሽ ሚኖራቸው? በል እስቲ ንገረኝ?”
ጥላዬ፣ ሊቀጥለው የማይችልበት ሙግት ሆነበትና ዝም አለ።
አብርሃን በዐይኑ ፈልጎ ሲያገኘው አብርሃ የአንገቱ ስሮች እስኪገታተሩ ድረስ ከሁለት ሰዎች ጋር ይከራከራል። ጥቂት ጠብቆት ወደቤቱ ሄደ።
ቤት ሲደርስ፣ አለቃ ሔኖክ ከሰዐት በኋላ እንደሚያደርጉት ጥላ ስር
ተቀምጠው ቀለም ይቀምማሉ። አጠገባቸው ሄዶ ተቀመጠ።
“የት ቆይተህ ነው?” አሉት
“ከአብርሃ ጋር ጃን ተከል ወርደን የሰዉ ክርክር ለብቻው
አላቸው።
“ስለምን ነው ሚከራከሩ?”
“ስለ እቴጌ...” ምንትዋብ ይበላት ወለቴ ቸገረው። ገና ምንትዋብ
የሚለውን ስም አልተለማመደውም። “እቴጌዋ አርግዘዋልና ወንድ በሆነ
እያለ ሰዉ ይነታረካል።”
“መቸም ውነት ነው። ለእቴጌም ሆነ ለንጉሡ ወንድ መሆኑ ይጠቅማል።በዝኸ ግዝየ እቴጌስ ቢሆኑ ተኝተው ያድሩ መሰለህ? ቤተመንግሥት ውስጥ ያለ ወሬ ስንኳ አያስተኛቸውም። ወንድ ቢሆንላቸው ንጉሡን የሳቸው ደጋፊ የሆኑትን መኳንንት ጭምር ያስደስታሉ። እሳቸውም
ልባቸው ያርፋል።”
“ፈርዶባቸዋላ!”
“እዝጊሃር ይርዳቸው። በዝኸ ላይ ኸቋራ ናቸው።”
“ኸቋራ ቢሆኑ ምን ሞገድ አለው?”
“አየ ጥላዬ! አለው እንጂ። በአንድ በኩል መኳንንቱ የቋራ ደም
ያለው አልጋው ላይ እንዲወጣ አይፈልጉም። ቋራ እንደ ጐንደር
ማዶል። ባላገር ነው ብለው ያስባሉ። በሌላ በኩል ደሞ እወህኒ አምባ ስንቱ የነጋሢ ዘር መሰለህ አሰፍስፎ ሚወለደው ወንድ ይሁን ሴት ሚጠባበቀው። ወንድ ኸተወለደ የመንገሥ ዕድላችን ይዘገይብናል
አለያም ያመልጠናል ብለው ይሰጋሉ። ሴት የሆነች እንደሁ እነሱም ይደሰታሉ፣ ከንጉሡ ጋር ጠብ ያላቸው መኳንንትም የልባቸው ይደርሳል። ንጉሡም ቢሆኑ ዳግም ሴት ኸተወለደችላቸው ያዝናሉ።
አየህ ነገሥታቱ አልጋቸውን አሳልፈው መስጠት ስለማይፈልጉ ወንድ ልዥ ለማግኘት ሲሉ ዕቁባት ይይዛሉ። አሁን አጤ ቴዎፍሎስ...
የታላቁ ኢያሱ ወንድም፣ የጃንሆይ አጎት መሆናቸው ነው... ከሕግ
ባለቤታቸው ኸእቴጌ ወለተጽዮን ጠንተው ሲኖሩ እቴጌዋ መካን ነበሩና አልጋ ሚወርስ ልዥ አልነበራቸውም። ስለዝኸ የነጋሲ ዘር የሌላቸው የአጤ ቴዎፍሎስ እንደራሴ የነበሩት ዮስጦስ ነገሡ። አሁንም ጃንሆይ ቢሞቱ ስንኳ አልጋቸውን ሚወርስ ልዥ የለም። ለዝኸ ነው ያ ሁሉ ክርክር።”
“እቴጌ ሴት ኸወለዱ ጉድ ነው ቢሉ ጉዱ ምኑ ላይ ነው ብል አንዱ ዥል የተዣዣለ ብሎ ሰደበኝ” አላቸው፣ እየሳቀ።
አለቃ ሔኖክ እንባቸው ጠብ እስኪል ሳቁና፣ “እንግዲህ ለእቴጌ
እንጸልይላቸዋለን” አሉት።
ኧረ አጥብቄ ጸልይላታለሁ አለ፣ ለራሱ።......
✨ይቀጥላል✨
👍15
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...«አምጡት እንግዲው!» አላች ታፈሡ በልሁና መርዕድን በፈገግታ አይን እያየቻቸው።.
መርዕድ አልዘገየም፤ የመቃሚያውን ቦታ በአዲስ መልክ አበጃጀው ጫቱን ከጋዳ ውስጥ አወጣ። ያ ቤት እንደገና ነፍስ ዘራ። የጫቱ መጀመር በተለይ በታፈሡና በሔዋን እናት መካከል ተጨማሪ ውይይት እንዲፈጠር ምክንያት ሆነ።
«በልሁ» ስትል ታፈሡ መጀመሪያ ጠራችው፡፡
«አቤት»
«የሒዩ እናት ትናንት ሸዌዬ ቤት እንዳደሩ ነገሩኝ፡፡ ነገር ግን ደስ ያላቸው አልመስለኝም፡፡» አለች በተለይ የሔዋንን እናት አየት እያደረገች::
«ከፋዎት እንዴ እማማ?» ሲል ጠየቃቸው በልሁ፡፡ቢከፋኝስ የት እደርሳለሁ ብለህ የኔ ልጅ አሉ የሔዋን እናት ጉንበሰ ብለው መሬት መሬት እያዩ።
ቀድሞ ነገር በልጅዎ ቤት ለምን ይከፋዎታል? አለ በልሁ አሁንም፡፡
«ምኑን አወቅት ብለህ የኔ ልጅ! እንግዲህ እያደር ሳውቀው ይገባኝ እንደሆነ እንጂ እስታሁንስ ነገሩ ሁሉ ግራ ግብት ነው ያለኝ» አሉ የሔዋን እናት::
ታፈሡ ወደ ሔዋን አየት እያረገች ሔዩ! ለእማማ ሁሉንም ነገር
ልነግራቸው ነው ከፋሽስት አልከፋሽ የራስሽ ጉዳይ» አለቻት በመቀለድ ዓይነት
ሔዋን አንገቷን ወደ መሬት ቀበረች፡፡ እናቷ ሳይቀሩ በልሁ፣ መርዕድና ታፈሡም ያዩዋት ጀምር። በዚህ ግዜ እናቷ፣
ነውር የሆነ ነገር ሰራሽ እንዴ እመ'ዩ?» ሲሉ ጠየቋት፡፡
የእርስዎ ልጄ ነወር ልትሰራ አልተፈጠረችም::» አለች ታፈሡ እንደገና ወደ በልሁና መርዕድ ዞር ብላ «ያ ሲያስጨንቀን የነበረ ሸዋዬ ስለ ሔዋን ለወላጆቿ
የፃፈችው ደብዳቤ እኮ አልተላከልንም» አሉ አለቻቸው ሁለቱንም አየት አየት
እያረገቻቸው
«ሙት በይኝ» አለ በልሁ።
አያችሁ! ሔዩም ስትጨነቅ፣ አስቻለውም እኛም ስንታመስ የኖርነው እንዲሁ በከንቱ ኖሯል» አለችና የተፃፈው ደብዳቤ ይዘት ምን እንደነበረ ዘርዘር አድርጋ ለሔዋን እናት አሰረዳቻቸው፡፡ ሸዋዬ ያን ደብዳቤ ሔዋንን ለማስፈራራትና ለማስደንገጥ እንጂ ልትልከው እስባ እንዳልነበር እንደ አዲስ ታሰባቸው፡፡
የሔዋን እናት የደብዳቤውን ይዘት ከታፈሡ ገለፃ ከተረዱ በኋላ “ይህን ነገር እሙዬ ፈፅማው ነው ወይስ ...» ብለው ታፈሡም ሔዋንንም ሲመለከቱ ታፈሡ ራሷ ቀጠለች::
«አዩ እማማ! መቸም ሔዩም ሽዋዬም ልጆችዎ ናቸው። በእርስዎ ፊት አንዷን ወግነን ሌላዋን ብናማ ትዝብት እንደሆነ እንጂ ሌላ እንደማናተርፍ
እናውቃለን፡፡ ግን ደግሞ እውነቱን ግልጥልጥ አድርገን ልንነግርዎት እንፈልጋለን።አለቻቸው አንድ የጫት እግር ይዛ ወዝወዝ ወዝወዝ እያደረገች፡፡
«በጄ» አሏት የሔዋን እናት ለነገሩ እየጓጉ።
«ሔዩና ሽዋዬ በሚያጣላ ነገር ተጣልተው ለማስታረቅ ብዙ ጥረን ነገር ግን በሸዋዬ እምቢተኝነት ሳይሳካልን ቀረ፡፡
«ምን አጣላቸው የኔ ልጅ?»
ታፈሡ ነገሩን ከሥሩ ጀመረችላቸው በቅድሚያ እሷና ሸዋዪ የትና እንዴት እንደሚተዋወቁ ሸዋዬ ከያቤሎ
ወደ ዲላ ስትመጣ ያደረገችላትን
አቀባበለ፤ ቀጥላም የእስቻለውን ምንነትና ማንነት፤ ከእሷ ጋር የነበረውን ግንኝነትም እንዲሁ ገለፀችላቸው፡፡ በመጨረሻም የአስቻለውንና የሔዋንን ጉዳዩ
ከአጀማመሩ እስከ የወደፋት አላማቸው ድረስ አስረዳቻቸው
ለዚህ ነገር የሸዋዬ አቋም ምን ይመስል እንደነበር ችግሩን ለመፍታት የተደረገውንና ሊደርግ
የነበረውን ጥረት ሁሉ ዘረዘረቾላቸው።
የሔዋን እናት በነገሩ መመሰጣቸው የተነሳ በወሬው መሀል ቢጠሯቸው
እንኳ "ወያ" የሚሉ አይመስሉም፡። እንዲያውም እንባቸው እየመጣ በለበሱት ነጠላ ዓይናቸውን ጨመቅ ያደርጋሉ፡፡ ሔዋንንም ዞር እያሉ ስሜቷን ሲሰልሉ እንባዋ
በጉንጯ ላይ ሲፈስ ያያሉ በዚያው ልክ ሆዳቸው ይንቦጫቦጫል የእሳቸው ሁኔታ የሁሉንም ቀልብ ስቦ ሁሉም በትካዜ አስተያየት ያዩአቸዋል፡፡
ታፈሡ አሁንም የሔዋንና የሸዋዬን ለየብቻ የመኖር ምክንያት ልትጠቁማቸው ፈልጋ ሸዋዬ ሔዋንና አስቻለውን ለመለያየት ያደረገችውን ጥረትና ሔዋንም በማትፈልገው ሰው ልታስደፍራት መሞከሯን ጭምር ነገረቻቸው።
የሔዋን እናት ነገሩ ሁሉ ግርም አላቸውና «እንዴት ነው ይኸ ነገር
እሙዬ» ሲሉ በተላይ ሔዋንን እያዩ ጠየቋት፡፡ ምናልባት እሷም በሆዷ ውስጥ ያለ ነገር ካለ ብለው ብትነግራቸው ፈለጉ።
«ሔዋን ፤ ኢይዞሽ ንገሪያቸው!» አለች ታፈሡ በልጃቸው አንደበት ቢሰሙ የበለጠ ላያምኑ እንደሚችሉ በመገመት።
ሔዋን ግን አልቻለችም። ለቅሶ ቀደማትና በእናቷ “ጭን ላይ ድፍት በማለት ትንሰቀሰቅ ጀመር፡፡ እናቷም ታፈሡም ቢያባብሏት ዝም ልትል አልቻለችም በመሀል በልሁ ተቆጣት።
“እንቺ ሔዋን» አለና ከመቀመጫው ብድግ አለ፡፡ «ቀና ብለሽ ቁጭ በይ።ለምን የእናትሽን ሆድ ታባቢያለሽ?» አለና አንገቷን ደገፍ አድርጐ ቀና አደረጋት፡፡
«እናትሽ የጠየቁሽን መልሽላቸው።» አላት እንደገና።
«አ- አንቺ ን- ንገሪያት ታፈሡዪ!» አለች ሔዋን ድምጿ እየተቆራረጠ፡፡ታፈሡ ቀጠለች:: በመሀል ደሞ አንድ ችግር ተፈጠረብን እማማ። ይህ
እስቻለው ያልከዎት ወንድማችን ሳያሰበው በዘመቻ ስም በግዳጅ ወደ ኤርትራ መሄድ ግድ ሆነበት።
ይህም አጋጣሚ የተፈጠረው በሸዋዬ አማካኝነት ልጁንና
ሔዋንን ለመነጣጠል የተዶለተ ሴራ መስሉ ታየንና ሔዋን ያለ ፍላጎቷ ከመደፈሯ በፊት ማሸሽ ፈለግን። ልጁም ደሞዙን ለእሷ መተዳደርያ እንዲሆን አድርጎ ስለነበረ ከሽዋዬ ቤት ወጥታ እዚህ ቤት እንድትኖር አደረግን፡፡ በቃ ሔዋን ከሸዋዬ ቤት የወጣችብት ምስጢሩ ይህ ነው የኔ እናት» አለቻቸውና ምላሻቸውን በመጠበቅ ዓይኗን በዓይኖቻቸው ላይ ስክት አደረገቻቸው።
ለልጁ መዝመት መዘዘኛዋ ያቸው የእኔ ልጅ ናት በይኛ» አሉና የሔዋን እናት ታፈሡን ያዩዋት ጀመር።
«እውነተኛውን ነገር እግዜር ይወቅ እማማ በኛ በኩል ግን እንደዚያ
ገመትን፡፡» አለችና ታፈሡ እጆቿን ጨብጣ አገጯን በማስደገፍ የሔዋንን እናት እየተመለከተች «አስቻለው ከመስሪያ ቤት አለቃው ጋር አይስማማም ነበር። ሽዋዬ
ደግሞ ከዚያ ሰው ጥብቅ የሆነ ግንኙነት ፈጠረች፡፡ እኛም በዚህ ጉዳይ የተነጋገሩበትና በጋራ የፈጠሩት መላ ሊሆን እንደሚችል ጠረጠር።አለቻቸው
የሔዋን እናት ያላሰቡት ስሜት ተፈጠረባቸው፡፡ በግራ እጅ መዳፋቸው ጉንጫቸውን ደገፍ አድርገው «እየየ እኔ! እየየ እኔ! ..» በማለት የተሰማቸውን ሃዘን ሲገልፁ እንባቸውም ከአይናቸው ላይ ድንቡቅ ብሎ ወረደ በዚህ ጊዜ በልሁ ብድግ ብሎ ወደ ጓዳ ገባና ቀድሞ የአስቻለው አሁን ደግሞ የሔዋን ከሆነው አልጋ የራስጌ ኮመዲኖ ላይ ሁለት ትላልቅ ፎቶግራፎች ይዞ ተመለሰ አንዱ አስቻለው ለብቻው የተነሳው ሌላው ደግሞ ወደ ኤርትራ ከመሄዱ አንድ ቀን በፊት ከሔዋን ጋር በመሆን በቁም የተነሱት ነበር። ሁለቱንም ፎቶግራፎች ለሔዋን እናት እየሰጠ እዩት እማማ! «ልጁም ይህ ነበር» አላቸው።
የሔዋን እናት ፎቶግራፎቹን በጭናቸው ላይ አስቀምጠው ልክ እንደ ፊት መስታወት እያዩ በቀኝ እጃቸው ቡጢ ደረታቸውን ደስቅ ደሰቅ እያደረጉ እ - እ እ ካሉ በኋላ ዓይኔ ይፍለስ! ዓይኔ ይፍስስ! ዓይኔ ይፍሰስ» አሉና «ምነው ይኽን ጉድ ሳነልሰማ ሞቼ አርፊው ቢሆን!» በማለት ከሁንም ዓይንና አፍንጫቸውን በነጠላቸው ይጠራቸው ጀመር።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...«አምጡት እንግዲው!» አላች ታፈሡ በልሁና መርዕድን በፈገግታ አይን እያየቻቸው።.
መርዕድ አልዘገየም፤ የመቃሚያውን ቦታ በአዲስ መልክ አበጃጀው ጫቱን ከጋዳ ውስጥ አወጣ። ያ ቤት እንደገና ነፍስ ዘራ። የጫቱ መጀመር በተለይ በታፈሡና በሔዋን እናት መካከል ተጨማሪ ውይይት እንዲፈጠር ምክንያት ሆነ።
«በልሁ» ስትል ታፈሡ መጀመሪያ ጠራችው፡፡
«አቤት»
«የሒዩ እናት ትናንት ሸዌዬ ቤት እንዳደሩ ነገሩኝ፡፡ ነገር ግን ደስ ያላቸው አልመስለኝም፡፡» አለች በተለይ የሔዋንን እናት አየት እያደረገች::
«ከፋዎት እንዴ እማማ?» ሲል ጠየቃቸው በልሁ፡፡ቢከፋኝስ የት እደርሳለሁ ብለህ የኔ ልጅ አሉ የሔዋን እናት ጉንበሰ ብለው መሬት መሬት እያዩ።
ቀድሞ ነገር በልጅዎ ቤት ለምን ይከፋዎታል? አለ በልሁ አሁንም፡፡
«ምኑን አወቅት ብለህ የኔ ልጅ! እንግዲህ እያደር ሳውቀው ይገባኝ እንደሆነ እንጂ እስታሁንስ ነገሩ ሁሉ ግራ ግብት ነው ያለኝ» አሉ የሔዋን እናት::
ታፈሡ ወደ ሔዋን አየት እያረገች ሔዩ! ለእማማ ሁሉንም ነገር
ልነግራቸው ነው ከፋሽስት አልከፋሽ የራስሽ ጉዳይ» አለቻት በመቀለድ ዓይነት
ሔዋን አንገቷን ወደ መሬት ቀበረች፡፡ እናቷ ሳይቀሩ በልሁ፣ መርዕድና ታፈሡም ያዩዋት ጀምር። በዚህ ግዜ እናቷ፣
ነውር የሆነ ነገር ሰራሽ እንዴ እመ'ዩ?» ሲሉ ጠየቋት፡፡
የእርስዎ ልጄ ነወር ልትሰራ አልተፈጠረችም::» አለች ታፈሡ እንደገና ወደ በልሁና መርዕድ ዞር ብላ «ያ ሲያስጨንቀን የነበረ ሸዋዬ ስለ ሔዋን ለወላጆቿ
የፃፈችው ደብዳቤ እኮ አልተላከልንም» አሉ አለቻቸው ሁለቱንም አየት አየት
እያረገቻቸው
«ሙት በይኝ» አለ በልሁ።
አያችሁ! ሔዩም ስትጨነቅ፣ አስቻለውም እኛም ስንታመስ የኖርነው እንዲሁ በከንቱ ኖሯል» አለችና የተፃፈው ደብዳቤ ይዘት ምን እንደነበረ ዘርዘር አድርጋ ለሔዋን እናት አሰረዳቻቸው፡፡ ሸዋዬ ያን ደብዳቤ ሔዋንን ለማስፈራራትና ለማስደንገጥ እንጂ ልትልከው እስባ እንዳልነበር እንደ አዲስ ታሰባቸው፡፡
የሔዋን እናት የደብዳቤውን ይዘት ከታፈሡ ገለፃ ከተረዱ በኋላ “ይህን ነገር እሙዬ ፈፅማው ነው ወይስ ...» ብለው ታፈሡም ሔዋንንም ሲመለከቱ ታፈሡ ራሷ ቀጠለች::
«አዩ እማማ! መቸም ሔዩም ሽዋዬም ልጆችዎ ናቸው። በእርስዎ ፊት አንዷን ወግነን ሌላዋን ብናማ ትዝብት እንደሆነ እንጂ ሌላ እንደማናተርፍ
እናውቃለን፡፡ ግን ደግሞ እውነቱን ግልጥልጥ አድርገን ልንነግርዎት እንፈልጋለን።አለቻቸው አንድ የጫት እግር ይዛ ወዝወዝ ወዝወዝ እያደረገች፡፡
«በጄ» አሏት የሔዋን እናት ለነገሩ እየጓጉ።
«ሔዩና ሽዋዬ በሚያጣላ ነገር ተጣልተው ለማስታረቅ ብዙ ጥረን ነገር ግን በሸዋዬ እምቢተኝነት ሳይሳካልን ቀረ፡፡
«ምን አጣላቸው የኔ ልጅ?»
ታፈሡ ነገሩን ከሥሩ ጀመረችላቸው በቅድሚያ እሷና ሸዋዪ የትና እንዴት እንደሚተዋወቁ ሸዋዬ ከያቤሎ
ወደ ዲላ ስትመጣ ያደረገችላትን
አቀባበለ፤ ቀጥላም የእስቻለውን ምንነትና ማንነት፤ ከእሷ ጋር የነበረውን ግንኝነትም እንዲሁ ገለፀችላቸው፡፡ በመጨረሻም የአስቻለውንና የሔዋንን ጉዳዩ
ከአጀማመሩ እስከ የወደፋት አላማቸው ድረስ አስረዳቻቸው
ለዚህ ነገር የሸዋዬ አቋም ምን ይመስል እንደነበር ችግሩን ለመፍታት የተደረገውንና ሊደርግ
የነበረውን ጥረት ሁሉ ዘረዘረቾላቸው።
የሔዋን እናት በነገሩ መመሰጣቸው የተነሳ በወሬው መሀል ቢጠሯቸው
እንኳ "ወያ" የሚሉ አይመስሉም፡። እንዲያውም እንባቸው እየመጣ በለበሱት ነጠላ ዓይናቸውን ጨመቅ ያደርጋሉ፡፡ ሔዋንንም ዞር እያሉ ስሜቷን ሲሰልሉ እንባዋ
በጉንጯ ላይ ሲፈስ ያያሉ በዚያው ልክ ሆዳቸው ይንቦጫቦጫል የእሳቸው ሁኔታ የሁሉንም ቀልብ ስቦ ሁሉም በትካዜ አስተያየት ያዩአቸዋል፡፡
ታፈሡ አሁንም የሔዋንና የሸዋዬን ለየብቻ የመኖር ምክንያት ልትጠቁማቸው ፈልጋ ሸዋዬ ሔዋንና አስቻለውን ለመለያየት ያደረገችውን ጥረትና ሔዋንም በማትፈልገው ሰው ልታስደፍራት መሞከሯን ጭምር ነገረቻቸው።
የሔዋን እናት ነገሩ ሁሉ ግርም አላቸውና «እንዴት ነው ይኸ ነገር
እሙዬ» ሲሉ በተላይ ሔዋንን እያዩ ጠየቋት፡፡ ምናልባት እሷም በሆዷ ውስጥ ያለ ነገር ካለ ብለው ብትነግራቸው ፈለጉ።
«ሔዋን ፤ ኢይዞሽ ንገሪያቸው!» አለች ታፈሡ በልጃቸው አንደበት ቢሰሙ የበለጠ ላያምኑ እንደሚችሉ በመገመት።
ሔዋን ግን አልቻለችም። ለቅሶ ቀደማትና በእናቷ “ጭን ላይ ድፍት በማለት ትንሰቀሰቅ ጀመር፡፡ እናቷም ታፈሡም ቢያባብሏት ዝም ልትል አልቻለችም በመሀል በልሁ ተቆጣት።
“እንቺ ሔዋን» አለና ከመቀመጫው ብድግ አለ፡፡ «ቀና ብለሽ ቁጭ በይ።ለምን የእናትሽን ሆድ ታባቢያለሽ?» አለና አንገቷን ደገፍ አድርጐ ቀና አደረጋት፡፡
«እናትሽ የጠየቁሽን መልሽላቸው።» አላት እንደገና።
«አ- አንቺ ን- ንገሪያት ታፈሡዪ!» አለች ሔዋን ድምጿ እየተቆራረጠ፡፡ታፈሡ ቀጠለች:: በመሀል ደሞ አንድ ችግር ተፈጠረብን እማማ። ይህ
እስቻለው ያልከዎት ወንድማችን ሳያሰበው በዘመቻ ስም በግዳጅ ወደ ኤርትራ መሄድ ግድ ሆነበት።
ይህም አጋጣሚ የተፈጠረው በሸዋዬ አማካኝነት ልጁንና
ሔዋንን ለመነጣጠል የተዶለተ ሴራ መስሉ ታየንና ሔዋን ያለ ፍላጎቷ ከመደፈሯ በፊት ማሸሽ ፈለግን። ልጁም ደሞዙን ለእሷ መተዳደርያ እንዲሆን አድርጎ ስለነበረ ከሽዋዬ ቤት ወጥታ እዚህ ቤት እንድትኖር አደረግን፡፡ በቃ ሔዋን ከሸዋዬ ቤት የወጣችብት ምስጢሩ ይህ ነው የኔ እናት» አለቻቸውና ምላሻቸውን በመጠበቅ ዓይኗን በዓይኖቻቸው ላይ ስክት አደረገቻቸው።
ለልጁ መዝመት መዘዘኛዋ ያቸው የእኔ ልጅ ናት በይኛ» አሉና የሔዋን እናት ታፈሡን ያዩዋት ጀመር።
«እውነተኛውን ነገር እግዜር ይወቅ እማማ በኛ በኩል ግን እንደዚያ
ገመትን፡፡» አለችና ታፈሡ እጆቿን ጨብጣ አገጯን በማስደገፍ የሔዋንን እናት እየተመለከተች «አስቻለው ከመስሪያ ቤት አለቃው ጋር አይስማማም ነበር። ሽዋዬ
ደግሞ ከዚያ ሰው ጥብቅ የሆነ ግንኙነት ፈጠረች፡፡ እኛም በዚህ ጉዳይ የተነጋገሩበትና በጋራ የፈጠሩት መላ ሊሆን እንደሚችል ጠረጠር።አለቻቸው
የሔዋን እናት ያላሰቡት ስሜት ተፈጠረባቸው፡፡ በግራ እጅ መዳፋቸው ጉንጫቸውን ደገፍ አድርገው «እየየ እኔ! እየየ እኔ! ..» በማለት የተሰማቸውን ሃዘን ሲገልፁ እንባቸውም ከአይናቸው ላይ ድንቡቅ ብሎ ወረደ በዚህ ጊዜ በልሁ ብድግ ብሎ ወደ ጓዳ ገባና ቀድሞ የአስቻለው አሁን ደግሞ የሔዋን ከሆነው አልጋ የራስጌ ኮመዲኖ ላይ ሁለት ትላልቅ ፎቶግራፎች ይዞ ተመለሰ አንዱ አስቻለው ለብቻው የተነሳው ሌላው ደግሞ ወደ ኤርትራ ከመሄዱ አንድ ቀን በፊት ከሔዋን ጋር በመሆን በቁም የተነሱት ነበር። ሁለቱንም ፎቶግራፎች ለሔዋን እናት እየሰጠ እዩት እማማ! «ልጁም ይህ ነበር» አላቸው።
የሔዋን እናት ፎቶግራፎቹን በጭናቸው ላይ አስቀምጠው ልክ እንደ ፊት መስታወት እያዩ በቀኝ እጃቸው ቡጢ ደረታቸውን ደስቅ ደሰቅ እያደረጉ እ - እ እ ካሉ በኋላ ዓይኔ ይፍለስ! ዓይኔ ይፍስስ! ዓይኔ ይፍሰስ» አሉና «ምነው ይኽን ጉድ ሳነልሰማ ሞቼ አርፊው ቢሆን!» በማለት ከሁንም ዓይንና አፍንጫቸውን በነጠላቸው ይጠራቸው ጀመር።
👍9❤1
«አይቀየሙኝኛ» አለ በልሁ ሔዋንና ሽዋዬ ከአንድ እናት ማህፀን የወጡ
አይመስለኝም እማማ ቅር ይልዎት ይሆን?» ሲል ጠየቃቸው፡፡
«የእናት ሆድ ዥንጉርጉር የተባለው ስለዚህ አይደል የኔ ልጅ! አንተም
በኔም ሆድ ብዙ አለ፡፡» አሉና ድንገት በሀሳብና በትካዜ ውስጥ ጭልጥ ብለው ገቡ።
የሸዋዬን የልጅነት አስተዳደግ እያስታወሱ ነው፡፡ ሽዋዬ በህፃንነቷ ገና በእቅፋቸው ውስጥ ሆና ጡታቸውን ጠብታ ጠብታ ስትጠግብ እንዴት አድርጋ ትነክሳቸው እንደነበር ትዝ አላቸው፡፡ ጠንክር ብላ ወደ ውጭ
መውጣት ስትጀምር ደግሞ
ከጎረቤት ልጆች ጋር ባለመስማማት ወይ አልቅሳ አለያም አስለቅሳ በመመለስ
የምታመጣባቸውን ስሞታ ሁሉ አስታወሱ። በቤት ውስጥ ደግሞ አጥፊ አውዳሚ፣ ምንም ነገር፣ የትም ቦታ ቢደበቅ የማያመልጣት ሰርሳሪ በዚያ ላይ ደግሞ ሰባቂ፣ የእናቷን ሚስጢር ለአባቷ፣ የአባቷን ደግሞ ለእናቷ እየነገረች
የምታሳጣቸው ሰላም እንኳ እልቀራቸውም፡፡ “ይቺ መሄጃዋ የማይታወቅ መዘዘኛ እያሉ ገና በልጅነቷ ይማረሩባት የነበረው ሁሉ ትዝ አላቸው።
ለአፍታ ያህል ፀጥታ ሰፈነና ከቆይታ በኋላ ግን የፀጥታውን ድባብ ራሳቸው' የሔዋን እናት ቀድመው ሰበሩት፡፡ ለመሆኑ ልጁ መቼ ይሆን የሚመለሰው?» ሲሉ ጠየቋቸው።
ታፈሡና በልሁ ድንገት ድንግጥ ድንግጥ አሉና እርስ በርስ ተያዩ።
መርዕድ ግን ከእነሱ በባሰ ሁኔታ ደንግጦ ውጭ ውጭ ያይ ጀመር፡፡
«ግራ ገብቶናል እማማ::» አለች ታፈሡ እሷም ብትሆን ቀጥላ የምትለው ነገር አስፈርቷት መሬት መሬት እያየች፡፡
«እንዴት የኔ ልጅ?»
የሄደው ለስድስት ወር ተብሎ ነበር፤ አሁን ግን ይኸው ዓመት ሊሞላው ነው። ግን እልም ብሎ ጠፍቶብን በሀሳብ ላይ ነው ያለነው::» አለችና ወደ በልሁ
ዞር ብላ ምናልባት ግን ሰሞኑን አንድ ነገር ስምተናልና የተስፋ ጭላንጭል ነው ብለን ገምተናል ብላ በልሁን 'ተናገር' በሚል ስሜት
በዓይኗ ጠቀስ አደረገቻቸው ተግባብተዋልና በልሁ ቀጠለ።
«ይህን ነገር ለሔዋንም ልንነግራት ነበር ዛሬ የተሰበሰብነው ሲል ጀመረ። «ደሞዙን ከመስሪያ ቤቱ እያመጣሁ ለሔዋን የምሰጣት እኔ ነበርኩ። ከጥቂት ቀናት በፊት ሄጄ ስጠይቅ ግን ደሞዝ ተቋርጧል የሚል ወሬ ሰማሁ፡፡» አለና ቀና ብሎ ሔዋንና እናቷን እየተመለከተ
ያን ቀደም ሲል ከእነታፈሡ ጋር ሆነው የፈጠሩትን ሔዋንን የማረጋጊያ ዘዴ መተረክ ጀመረ። አስቻለው በምጽዋ በኩል ወደ ውጭ ሄዶ ሊሆን እንደሚችል፤ ጀርመን ወይም ጣሊያን ሀገር ገብቶ ሊሆን እንደሚችል
ደብዳቢው በቅርቡ ሊመጣ እንደሚችል …ወዘተ። በልሁ በዚህ ዙሪያ ብዙ ብዙ ተናገረ።
በዚህ ትረካ ምናልባት የሔዋን እናት ተታልለው ሊሆን ይችላል፣ ሔዋን ግን የአስቻለውን ደሞዝ መቋረጥ ስትሰማ አይኗቿ ወደ ዳር ወተው ተጎለጎሉ ትን ትንፋሿም በርከት በርከት ፈጠን ፈጠን ማለት ጀመረ:: ታፈሱና በልሁ ስሜቷ ገብቷቸው በፍርሃት አስተያየት ሲመለከቷት ሔዋን ድንገት ተናገረች.
«ምን እያልክ ነወ በልሁ?» ስትል ጠየቀችው፡፡
«አትጠራጠሪ ሔዋን፣ ይሄ ነገር ለበጉ ነው፡» አላት ምላሽ የምትሰጥ ከሆነ ብሎ አይን አይኗን እያየ።
የሔዋን ሁኔታ የበለጠ እያስፈራራ ሄደ። ዓይኖቿ እንደፈጠጡ ቀሩ፡፡
በታፈሡና በበልሁ እንዲሁም በመርዕድ ላይ አከታትላ ታንከራትታቸው ጀመር።ወዲያው ደግሞ በረጅሙ ተነፈሰችና ወደ መሬት አጎነበሰች 'ኤርትራ የሄደ ይመለሳል ብለሽ.." የሚለው የበድሉ አነጋገርም ድንገት ፊቷ ላይ ድቅን አለባት፡፡
የሔዋን እናት ልጃቸውና ጎደኞቿ የተግባቡት ነገር እንዳለ ገባቸው
«ለመሆኑ እናቱ በሕይወት አሉ?» ሲሉ ጠየቁ፡፡
«እናትም አባትም የለውም፣ ሁለቱም ሞተውበታል፡፡» አለች ታፈሡ፡፡
የሔዋን እናት ከንፈራቸውን መጥጠው ዝም አሉ፡፡ አገጫቸውን በመደገፍ ወደ መሬት አጎነበሱ፡፡ ለአፍታ ያህል እሁንም ፀጥታ ሰፈነ። በመሀል ታፈሡ አንድ ነገር ትዝ አላት፡፡ ወዲያውም ማደናገሪያ ይሆናል ብላ በማሰብ ሳይሆን አይቅርም በልሁና መርዕድ የገዙትን ሥጋ ከጓዳ ወደ ሳሎን አመጣችና የእራት ወጥ
ለመስራት መከታተፍ ጀመረች። ፀጥታው ግን አሁንም ቀጠለ፡፡
«ተጫወቱ እማማት» አለ በልሁ ከብዙ ቆይታ በኋላ፡፡
«ልጆቼ» ሲሉ የሔዋን እናት ሁሉንም በአንዴ ጠሯቸው::
«አቤት እማማ?» አለች ታፈሡ ቀድማ፡፡ ግን ሁሉም ቀና ቀና ብለው ያይዋቸው ጀመር
«ታዲያ የእሙዬን ነገር እንዴት ባደርግ ይሻላል?» ሲሉ ጠየቁ፡፡
«እንዴት?” እላቸው በልሁ።
«የልጁ መምጫ ቀን አልታወቀም አላችሁ፡፡ በያ ላይ ደሞዙ ተቋረጠ ነው የምትሉኝ:፡ ታዲያ ወይ ይዣት ልሂድ?» ሲሉ ፈራ ተባ እያሉ ጠየቁ፡፡
ሁሉም ደነገጡና ዝም ዝም አሉ፡፡ ግን ደግሞ እርስ በእርስ ተያዩ።
«አይሻልም ብላችሁ ነው ልጆቼ? ወይስ ቅር ይላችሁ ይሆን?»
ሔዋን ስትል ታፈሠ ጠራቻት። ከመደንገጧ የተነሳ እንጂ ወይ ብትላት ቀጥላ የምትናግሪውን ነገር ታፈሡ አላዘጋጀችም።
«እሄዳለሁ» አለች ሔዋን ድንገት ሳትታስብ፡፡
«እ» አለ በልሁም ድንገጥ ብሎ።
«አዎ ከእማዬ ጋር ወደ ሃገሬን እሄዳለሁ።»አለች ሔዋን አሁንም ድርቅ ባለ ስሜትና ማጠንከር ባለ አነጋገር።አይኖቿ ግን አሁንም እንደተጎለጎሉ ናቸው። አንዳች ከብር ውስጧን ያናወጠባት ትመስላለች በዚህ ጊዜ ያልታሰበ ድምጽ፤ ባልታሰበ አኳኋን ካልታሰበ ሰው ተሰማ
ትርፌ እኔስ እታለምዬ ብላ ልክ እንደ ልጅነቷ ግንባሯን በክንዷ ሸፍና እይይይ…" ብላ አለቀሰች፡፡
ተይ እንጂ! ምን ነካሽ? እኛ እያለን! እኛ እያለን!» በማለት ታፈሡም በልሁም መርእድም አከታትለው ተንጫጩባት
እሷ ግን ዝም አላለችም፡፡ እንዲያውም በለቅሶዋ መሀል ልክ ቤት ውስጥ እንደምትጠሪው አይነት “ጋሽ አስቻለው…!» ስትል በርቀትና በጩኸት ድምጽ ተጣራች። አስቻለው ወደ አስመራ፣ ሔዋን ወደ ክብረ መንግስት
ተነጣጥለው ሲሄዱ እሷ ጭር ባለ በረሃ ውስጥ ብቻዋን የቀረች መሰላት። ሆዷም ባባና ስቅስቅ ብላ አለቀሰች።
«ታፈሡዬ አለች ሔዋን በመሀል
በዚያው ድርቅ ባለ ስሜት ውስጥ ሆና።
«ወይ የኔ ቆንጆ»
ሔዋን ግን ጥሪዋን ቀጠለች፡፡ «በልሀዬ! መርዕድ!» አለች በማከታተል።
«ወይ! አቤት» አሏት ሁለቱም፡፡
ለእስቹ ፀልዩለት። ትርፍዬን ደግሞ አደራ!!» አለቻቸው።......
💫ይቀጥላል💫
አይመስለኝም እማማ ቅር ይልዎት ይሆን?» ሲል ጠየቃቸው፡፡
«የእናት ሆድ ዥንጉርጉር የተባለው ስለዚህ አይደል የኔ ልጅ! አንተም
በኔም ሆድ ብዙ አለ፡፡» አሉና ድንገት በሀሳብና በትካዜ ውስጥ ጭልጥ ብለው ገቡ።
የሸዋዬን የልጅነት አስተዳደግ እያስታወሱ ነው፡፡ ሽዋዬ በህፃንነቷ ገና በእቅፋቸው ውስጥ ሆና ጡታቸውን ጠብታ ጠብታ ስትጠግብ እንዴት አድርጋ ትነክሳቸው እንደነበር ትዝ አላቸው፡፡ ጠንክር ብላ ወደ ውጭ
መውጣት ስትጀምር ደግሞ
ከጎረቤት ልጆች ጋር ባለመስማማት ወይ አልቅሳ አለያም አስለቅሳ በመመለስ
የምታመጣባቸውን ስሞታ ሁሉ አስታወሱ። በቤት ውስጥ ደግሞ አጥፊ አውዳሚ፣ ምንም ነገር፣ የትም ቦታ ቢደበቅ የማያመልጣት ሰርሳሪ በዚያ ላይ ደግሞ ሰባቂ፣ የእናቷን ሚስጢር ለአባቷ፣ የአባቷን ደግሞ ለእናቷ እየነገረች
የምታሳጣቸው ሰላም እንኳ እልቀራቸውም፡፡ “ይቺ መሄጃዋ የማይታወቅ መዘዘኛ እያሉ ገና በልጅነቷ ይማረሩባት የነበረው ሁሉ ትዝ አላቸው።
ለአፍታ ያህል ፀጥታ ሰፈነና ከቆይታ በኋላ ግን የፀጥታውን ድባብ ራሳቸው' የሔዋን እናት ቀድመው ሰበሩት፡፡ ለመሆኑ ልጁ መቼ ይሆን የሚመለሰው?» ሲሉ ጠየቋቸው።
ታፈሡና በልሁ ድንገት ድንግጥ ድንግጥ አሉና እርስ በርስ ተያዩ።
መርዕድ ግን ከእነሱ በባሰ ሁኔታ ደንግጦ ውጭ ውጭ ያይ ጀመር፡፡
«ግራ ገብቶናል እማማ::» አለች ታፈሡ እሷም ብትሆን ቀጥላ የምትለው ነገር አስፈርቷት መሬት መሬት እያየች፡፡
«እንዴት የኔ ልጅ?»
የሄደው ለስድስት ወር ተብሎ ነበር፤ አሁን ግን ይኸው ዓመት ሊሞላው ነው። ግን እልም ብሎ ጠፍቶብን በሀሳብ ላይ ነው ያለነው::» አለችና ወደ በልሁ
ዞር ብላ ምናልባት ግን ሰሞኑን አንድ ነገር ስምተናልና የተስፋ ጭላንጭል ነው ብለን ገምተናል ብላ በልሁን 'ተናገር' በሚል ስሜት
በዓይኗ ጠቀስ አደረገቻቸው ተግባብተዋልና በልሁ ቀጠለ።
«ይህን ነገር ለሔዋንም ልንነግራት ነበር ዛሬ የተሰበሰብነው ሲል ጀመረ። «ደሞዙን ከመስሪያ ቤቱ እያመጣሁ ለሔዋን የምሰጣት እኔ ነበርኩ። ከጥቂት ቀናት በፊት ሄጄ ስጠይቅ ግን ደሞዝ ተቋርጧል የሚል ወሬ ሰማሁ፡፡» አለና ቀና ብሎ ሔዋንና እናቷን እየተመለከተ
ያን ቀደም ሲል ከእነታፈሡ ጋር ሆነው የፈጠሩትን ሔዋንን የማረጋጊያ ዘዴ መተረክ ጀመረ። አስቻለው በምጽዋ በኩል ወደ ውጭ ሄዶ ሊሆን እንደሚችል፤ ጀርመን ወይም ጣሊያን ሀገር ገብቶ ሊሆን እንደሚችል
ደብዳቢው በቅርቡ ሊመጣ እንደሚችል …ወዘተ። በልሁ በዚህ ዙሪያ ብዙ ብዙ ተናገረ።
በዚህ ትረካ ምናልባት የሔዋን እናት ተታልለው ሊሆን ይችላል፣ ሔዋን ግን የአስቻለውን ደሞዝ መቋረጥ ስትሰማ አይኗቿ ወደ ዳር ወተው ተጎለጎሉ ትን ትንፋሿም በርከት በርከት ፈጠን ፈጠን ማለት ጀመረ:: ታፈሱና በልሁ ስሜቷ ገብቷቸው በፍርሃት አስተያየት ሲመለከቷት ሔዋን ድንገት ተናገረች.
«ምን እያልክ ነወ በልሁ?» ስትል ጠየቀችው፡፡
«አትጠራጠሪ ሔዋን፣ ይሄ ነገር ለበጉ ነው፡» አላት ምላሽ የምትሰጥ ከሆነ ብሎ አይን አይኗን እያየ።
የሔዋን ሁኔታ የበለጠ እያስፈራራ ሄደ። ዓይኖቿ እንደፈጠጡ ቀሩ፡፡
በታፈሡና በበልሁ እንዲሁም በመርዕድ ላይ አከታትላ ታንከራትታቸው ጀመር።ወዲያው ደግሞ በረጅሙ ተነፈሰችና ወደ መሬት አጎነበሰች 'ኤርትራ የሄደ ይመለሳል ብለሽ.." የሚለው የበድሉ አነጋገርም ድንገት ፊቷ ላይ ድቅን አለባት፡፡
የሔዋን እናት ልጃቸውና ጎደኞቿ የተግባቡት ነገር እንዳለ ገባቸው
«ለመሆኑ እናቱ በሕይወት አሉ?» ሲሉ ጠየቁ፡፡
«እናትም አባትም የለውም፣ ሁለቱም ሞተውበታል፡፡» አለች ታፈሡ፡፡
የሔዋን እናት ከንፈራቸውን መጥጠው ዝም አሉ፡፡ አገጫቸውን በመደገፍ ወደ መሬት አጎነበሱ፡፡ ለአፍታ ያህል እሁንም ፀጥታ ሰፈነ። በመሀል ታፈሡ አንድ ነገር ትዝ አላት፡፡ ወዲያውም ማደናገሪያ ይሆናል ብላ በማሰብ ሳይሆን አይቅርም በልሁና መርዕድ የገዙትን ሥጋ ከጓዳ ወደ ሳሎን አመጣችና የእራት ወጥ
ለመስራት መከታተፍ ጀመረች። ፀጥታው ግን አሁንም ቀጠለ፡፡
«ተጫወቱ እማማት» አለ በልሁ ከብዙ ቆይታ በኋላ፡፡
«ልጆቼ» ሲሉ የሔዋን እናት ሁሉንም በአንዴ ጠሯቸው::
«አቤት እማማ?» አለች ታፈሡ ቀድማ፡፡ ግን ሁሉም ቀና ቀና ብለው ያይዋቸው ጀመር
«ታዲያ የእሙዬን ነገር እንዴት ባደርግ ይሻላል?» ሲሉ ጠየቁ፡፡
«እንዴት?” እላቸው በልሁ።
«የልጁ መምጫ ቀን አልታወቀም አላችሁ፡፡ በያ ላይ ደሞዙ ተቋረጠ ነው የምትሉኝ:፡ ታዲያ ወይ ይዣት ልሂድ?» ሲሉ ፈራ ተባ እያሉ ጠየቁ፡፡
ሁሉም ደነገጡና ዝም ዝም አሉ፡፡ ግን ደግሞ እርስ በእርስ ተያዩ።
«አይሻልም ብላችሁ ነው ልጆቼ? ወይስ ቅር ይላችሁ ይሆን?»
ሔዋን ስትል ታፈሠ ጠራቻት። ከመደንገጧ የተነሳ እንጂ ወይ ብትላት ቀጥላ የምትናግሪውን ነገር ታፈሡ አላዘጋጀችም።
«እሄዳለሁ» አለች ሔዋን ድንገት ሳትታስብ፡፡
«እ» አለ በልሁም ድንገጥ ብሎ።
«አዎ ከእማዬ ጋር ወደ ሃገሬን እሄዳለሁ።»አለች ሔዋን አሁንም ድርቅ ባለ ስሜትና ማጠንከር ባለ አነጋገር።አይኖቿ ግን አሁንም እንደተጎለጎሉ ናቸው። አንዳች ከብር ውስጧን ያናወጠባት ትመስላለች በዚህ ጊዜ ያልታሰበ ድምጽ፤ ባልታሰበ አኳኋን ካልታሰበ ሰው ተሰማ
ትርፌ እኔስ እታለምዬ ብላ ልክ እንደ ልጅነቷ ግንባሯን በክንዷ ሸፍና እይይይ…" ብላ አለቀሰች፡፡
ተይ እንጂ! ምን ነካሽ? እኛ እያለን! እኛ እያለን!» በማለት ታፈሡም በልሁም መርእድም አከታትለው ተንጫጩባት
እሷ ግን ዝም አላለችም፡፡ እንዲያውም በለቅሶዋ መሀል ልክ ቤት ውስጥ እንደምትጠሪው አይነት “ጋሽ አስቻለው…!» ስትል በርቀትና በጩኸት ድምጽ ተጣራች። አስቻለው ወደ አስመራ፣ ሔዋን ወደ ክብረ መንግስት
ተነጣጥለው ሲሄዱ እሷ ጭር ባለ በረሃ ውስጥ ብቻዋን የቀረች መሰላት። ሆዷም ባባና ስቅስቅ ብላ አለቀሰች።
«ታፈሡዬ አለች ሔዋን በመሀል
በዚያው ድርቅ ባለ ስሜት ውስጥ ሆና።
«ወይ የኔ ቆንጆ»
ሔዋን ግን ጥሪዋን ቀጠለች፡፡ «በልሀዬ! መርዕድ!» አለች በማከታተል።
«ወይ! አቤት» አሏት ሁለቱም፡፡
ለእስቹ ፀልዩለት። ትርፍዬን ደግሞ አደራ!!» አለቻቸው።......
💫ይቀጥላል💫
👍12❤1
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...ጥላዬ፣ ከአለቃ ሔኖክ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እየመሠረተ ሲመጣ፣ብዙ ጊዜ አብሯቸው መቀመጥና መጫወት ሥዕል ከመሣል ቀጥሎ የሚያስደስተው ነገር ሆነ። ወደፊትም እንደሳቸው ጥበበኛ መሆን አበክሮ ተመኘ። ላደረጉለት ሁሉ ሲያመሰግናቸው ቢውል አላጠግበው አለ።
“አለቃ ላረጉልኝ ሁሉ እመቤቴ ምላሹን ትስጥዎ” አላቸው፣ አንድ
ቀን እንደወትሮዋቸው ግቢ ውስጥ ተቀምጠው ሲያወሩ።
“እኔኮ ማስተምረው ኸተማሪዎቸ ጥቅም አገኛለሁ ብየ ማዶል። ልክ
መምህሬ የነበሩት አለቃ ወልደሰንበት ደከመኝ ሳይሉ፣ ሚያውቁትን ሁሌ ሳይሸሽጉ እንዳሳተማሩኝ ሁሉ ተማሮቸን ማስተማር ፈልጋለሁ።ዋጋየ እናንተ ተማሮቸ ጥሩ ተምራችሁ ለጌታችን ያላችሁን እምነት፣ ክብርና ፍቅር በሥራችሁ ስታሳዩ፣ የመጻሕፍትን ምሥጢር አንብባችሁና ተረድታችሁ በሥዕል ስትገልጡ ነው። ሥዕል ዋናው ዓላማው ቤተስኪያንን ማስጌጥ ማዶል። ሥዕል እኮ ታሪክ ነው ሚነግር፤
ሥዕሉ ራሱ እኮ ወንጌል ነው። ምእመኑ የመጻሕፍቱን ምሥጢር
አውያቁም፣ አያነቡም፡ አይረዱም። ስለዝኸ የእናንተ ሥራ የመጻሕፍቱን ምሥጢር... ወንጌሉን በሥዕል እንዲረዱና መንፈሳዊነት፣ አክብሮትና
ፍራት በልባቸው እንዲያድር ማረግ ነው። ባለፈው እንደነገርኩህ ካህናቱ አምስቱን አዕማደ ምሥጢር በንባብ በሐተታ ይማራሉ።ምእመኑ ግን በሥዕል ነው ሚማር። ቀዳሚው ምሥጢረ ሥጋዌ ነው፣ኸገብርኤል ብሥራት ትጀምራለኽ። ገብርኤል ማርያምን ትፀንሲ ይላታል። ኸዚያ ልደቱን ትሥላለኸ። ልደቱን ስትሥል ሰብአ ሰገል እረኞቹም አሉ። ግዝረቱን ደሞ ቀጥለኽ መሣል ነው፤ ስምዖን አለ አሉ፣ አድግና ላሕም አሉ... ጌታን በትንፋሻቸው ያሞቁት፣ መልአኩም አብሮ ሚጠቀስ፤ ዓይኖቼ ማዳንህን ስላዩ በል ውሰደኝ ብሎ ጸልዮ
ይሞታል ። ኸዚያ ምሥጢረ ጥምቀቱ፣ ተአምራቱ፣ ቃና ዘገሊላው፣ አስተምህሮቱ አለ። ኸዚያ ምሥጢረ ቁርባንን ትሥላለህ፤ ሥቅለቱን አብረህ። ቀጥለህ ትንሣኤውንና ዕርገቱን ትሥላለህ። መጻሕፍት
በስንትና ስንት ምዕራፍ ያካተቱትን ታሪክ ሠዓሊው በጥቂት ብራናዎች አሣምሮ ቀምሮ ያስቀምጠዋል። ስለዚህ ምሥጢራቱን፣ የቱ ቀድሞ
የትኛው ሚከተል መሆኑን መመርመር ያስፈልጋል፤ የቀለም ማሳመር ብቻ ለሠዓሊነት አይበቃም።”
ጥላዬ፣ በተመስጦ አዳመጠና “እሺ የንታ፤ ንባቤንም ሥራዬንም
ተግቼ እቀጥላለሁ፤ ቃለ ሕይወት ያሰማልኝ” አላቸው፣ ትምህርታቸውን ከልቡ አዳምጦ።
“ዋናው ነገር እሱ ነው... ትጋት” አሉት፣ ሌባ ጣታቸውን እያወዛወዙ። “አንተን ትጉ ሁነህ አግኝቸኻለሁ። ምን ስጦታ ያለው ቢሆን ትጋት የሌለው ተማሪ አልወድም። ሥዕል ችሎታ ቢኖርህ ትጋት ኻላሳየህ ለሥራህ ጥሩ አይሆንም። አሁን በየቦታው ያሉት የተከበሩት ሠዓሊዎች አለሱ ሌላ ንሮ የላቸውም። አንዳንድ ተማሪ ይመጣል ኸኔ ዘንድ።እንዳው ብቻ ጫር ጫር አርጎ ቤተክሲያን ውስጥ ገብቶ ሥዕል
መሣል ይፈልጋል። ይኸ እንዴት ብሎ ይሆናል? ሥዕል ቀልድ ነው
እንዴ? እኔማ እንደዚያ ያለውን ተማሪ ኸኔ ዘንድ አላቆየውም። አንተ ለሥዕልም ለቤተክሲያንም አትሆንም ብየ ነው ምሰደው። ችሎታ አለ ትጋት ምንድርነው? አይምሰልህ ጥላዬ ሥራን ትልቅ ደረጃ ሚያደርሰው ትጋት ነው። እኔስ ብሆን አንድ ተማሪ ትጋት ካላሳየ ኸሱ ጋር ስለምን
እደክማለሁ? እስቲ በል ንገረኝ?”
“ውነት ነው... ውነት ነው” አለ፣ ጥላዬ ራሱን በአዎንታ እየነቀነቀ።
ልቡ ተነካ። ሥዕል እየሣለ ቤተክርስቲያንን ማገልገል እንዳለበት ይመኝ እንጂ፣ እንደዚህ ጠለቅ ብሎ ነገሩን አስቦበት አያውቅም።በአካባቢው የሚያያቸውን ቤቶች፣ ሰዎችና እንስሳት ቤታቸው ግድግዳ
ላይ ሲሥል ቢቆይም፣ የሚሥላቸውን ምስሎች ለዘላለም ቀርጾ ማስቀመጥ ከሚመኛቸው ነገሮች አንዱና ዋነኛው ምንትዋብን ነው። በተለይም
ደግሞ ነጠላ ተከናንባ ከቤተክርስቲያን ስትወጣ ያያት የነበረውን።
“ለሥዕል ያለኝ መውደድ ለብቻ ነው። ኸርሶ ዘንድ መማሬ ደሞ
ይበልጥ እንድወደው አድርጎኛል።”
“እኔም ለሥዕል ይኸ ነው ተብሎ ማይነገር ፍቅር አለኝ” አሉት።
“አለሱ ሌላ ሕይወት የለኝም። ሥዕል ሳይ እመራመራለሁ። የሠራሁትን ሥራ መልሼ ሳየው 'በውነት ይኸን የሠራኹ እኔ ነኝ ወይስ በኔ እጅ ራሱ ባለቤቱ ሣለው ብዬ እደነቃለኹ። ሥዕል የእዝጊሃር ወይም የደቂቀ
አማልክቱ ሥራ እንጂ የእኛ የደካሞቹ ፍጥረት አይመስለኝም። ጥላዬ...ሥዕል እኮ እንደ ቅኔ ከሳቴ ብርሃን ነው... የተደበቀውን ምሥጢር ሁሉ ሚገልጥ... ብርሃን ሚሰጥ። ለዝኽ ነው ቅኔን ብዙ ሊቃውንት ልሳነ መላእክት ነው ሚሉት።
ጥላዬ፣ መስማማቱን ለማሳየት ራሱን ነቀነቀ። “የንታ ሥዕል ለመማር እንደዛ ስመኝ ቆይቸ አሁን መማር በመቻሌ ዕድለኛ ሁኛለሁ።”
“ዕድል ኸሰማይ አይወድቅም” አሉት፣ ፊታቸውን ወደሱ መልሰው።
“ዕድል እንደ ሥዕል ነው። ሚገባው ዘንድ ነው ሚኸድ። ማይሆነው... ዝግጁ ሁኖ ማይጠብቀው ዘንድ አይኸድም። ወይም ማይሆነውን አይጣራም። ዕድል ልክ እንደ ሥዕል ሚፈልገውን ያውቃል፣ አውቆም
ይጣራል፣ ወይም ራሱ ወደሱ ይኸዳል። እንዳንተ ያለውን... የነፍሱን ጥሪ ሚያቀውን ኻለበት ፈልጎ ያወጣዋል። አንተም ዛዲያ ስትፈልገው፣ እሱም ሲፈልግህ... ስትፈላለጉ ቆይታችሁ ተገናኛችሁ።”
“አየ የንታ የእዝጊሃር ቸርነት ተጨምሮበት ነው።”
እዝጊሃር እኮ ማትችለውን አይሰጥህም። ጎበዝ ብትሆን ነው የሰጠህ።”
ውነት ነው አለ፣ ለራሱ።
“አሁን ይልቅ ምመክርህ” አሉት፣ ሌባ ጣታቸውን እያወዛወዙ፣ “ደብረ ወርቅ ኸደህ ሌሎች አስተማሮች ዘንድ መማርን ነው። እንደ ሌላው ትምርት ሁሉ ሥዕል እየተዘዋወርህ ስትማር ብዙ ትምርት ትቀስማለህ፣
ችሎታህንም ታዳብራለህ። ደብረ ወርቅ ታላላቅ የሥዕል መምህሮች
አሉ። እኔ እንደምታየው እያረዥሁ ነው። ኸንግዲህ እንደድሮው
ማስተማር አልችልም። አንተንም ገና ሳይህ ቀልቤ ስላረፈብህ
ተቀበልኩህ እንጂ ማስተማር እተዋለሁ እያልሁ ነበር” አሉት።
“የንታ ኸርሶ ዘንድ በቆየሁ። ኸርሶ መለየቱ ይከብደኛል።”
“ምን ይደረግ። እየደከመኝ መጣሁ።”
“ኸዝሁ ሌላ መምር ዘንድ ብቆይስ?”
“ሊቀጠበብት ኣዳሙ ዘንድ ነው እንድትማር የፈለግሁት። አዳሙ
ወደር ማይገኝለት መምህር ነው። ለኔም የረዥም ግዝየ ወዳጄ
ነው። እስታሁንም ብዙ ተማሮቸን ወደሱ ልኬያለሁ። አንተም ኸሱ
ዘንድ እንድትማር ነው ምፈልግ። ትምርትህን ስትጨርስ ተመልሰህ
ትመጣለህ።”
ጥላዬ፣ ጐንደር የዕድል በር ከፈተችልኝ፣ አለቃን መምህሬ፣ ጐንደርን ቤቴ ብሎ ተመቻችቶ ተቀምጦ፣ እንደዚህ ዓይነቱ ዱብ ዕዳ ሲመጣበት ደነገጠ፤ ሆድ ባሰው፤ መንፈሱ ተረበሸ፤ ተስፋ ሊቆርጥ ቃጣው።ከአለቃ ሔኖክ ሥር ሆኖ ታላቅ ሠዓሊ ለመሆን ያደረበትን ምኞት፣ከቤቱ ሲወጣ የሥዕል ንጉሥ ለመሆን የነበረውን ሕልም ሁሉ ጉም ሸፈነው። ደብረ ወርቅ ይሂድ ወይንም እዛው ጐንደር ሌላ አስተማሪ ዘንድ ይማር ለመወሰን አቃተው፤ ግራ ገባው። ምንትዋብን በአካል
ባያገኛትም እንኳ ከእሷ ርቆ መኖሩ ደግሞ አሳሰበው፣ አሳዘነው።....
።።።።።።።።።።፡፡።።።።።።።።።።።።
“ቁስቋም ብዙ ነገር ሰጥታኛለች፣ ወንድ ልዥ ደሞ ብትሰጠኝ።”
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...ጥላዬ፣ ከአለቃ ሔኖክ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እየመሠረተ ሲመጣ፣ብዙ ጊዜ አብሯቸው መቀመጥና መጫወት ሥዕል ከመሣል ቀጥሎ የሚያስደስተው ነገር ሆነ። ወደፊትም እንደሳቸው ጥበበኛ መሆን አበክሮ ተመኘ። ላደረጉለት ሁሉ ሲያመሰግናቸው ቢውል አላጠግበው አለ።
“አለቃ ላረጉልኝ ሁሉ እመቤቴ ምላሹን ትስጥዎ” አላቸው፣ አንድ
ቀን እንደወትሮዋቸው ግቢ ውስጥ ተቀምጠው ሲያወሩ።
“እኔኮ ማስተምረው ኸተማሪዎቸ ጥቅም አገኛለሁ ብየ ማዶል። ልክ
መምህሬ የነበሩት አለቃ ወልደሰንበት ደከመኝ ሳይሉ፣ ሚያውቁትን ሁሌ ሳይሸሽጉ እንዳሳተማሩኝ ሁሉ ተማሮቸን ማስተማር ፈልጋለሁ።ዋጋየ እናንተ ተማሮቸ ጥሩ ተምራችሁ ለጌታችን ያላችሁን እምነት፣ ክብርና ፍቅር በሥራችሁ ስታሳዩ፣ የመጻሕፍትን ምሥጢር አንብባችሁና ተረድታችሁ በሥዕል ስትገልጡ ነው። ሥዕል ዋናው ዓላማው ቤተስኪያንን ማስጌጥ ማዶል። ሥዕል እኮ ታሪክ ነው ሚነግር፤
ሥዕሉ ራሱ እኮ ወንጌል ነው። ምእመኑ የመጻሕፍቱን ምሥጢር
አውያቁም፣ አያነቡም፡ አይረዱም። ስለዝኸ የእናንተ ሥራ የመጻሕፍቱን ምሥጢር... ወንጌሉን በሥዕል እንዲረዱና መንፈሳዊነት፣ አክብሮትና
ፍራት በልባቸው እንዲያድር ማረግ ነው። ባለፈው እንደነገርኩህ ካህናቱ አምስቱን አዕማደ ምሥጢር በንባብ በሐተታ ይማራሉ።ምእመኑ ግን በሥዕል ነው ሚማር። ቀዳሚው ምሥጢረ ሥጋዌ ነው፣ኸገብርኤል ብሥራት ትጀምራለኽ። ገብርኤል ማርያምን ትፀንሲ ይላታል። ኸዚያ ልደቱን ትሥላለኸ። ልደቱን ስትሥል ሰብአ ሰገል እረኞቹም አሉ። ግዝረቱን ደሞ ቀጥለኽ መሣል ነው፤ ስምዖን አለ አሉ፣ አድግና ላሕም አሉ... ጌታን በትንፋሻቸው ያሞቁት፣ መልአኩም አብሮ ሚጠቀስ፤ ዓይኖቼ ማዳንህን ስላዩ በል ውሰደኝ ብሎ ጸልዮ
ይሞታል ። ኸዚያ ምሥጢረ ጥምቀቱ፣ ተአምራቱ፣ ቃና ዘገሊላው፣ አስተምህሮቱ አለ። ኸዚያ ምሥጢረ ቁርባንን ትሥላለህ፤ ሥቅለቱን አብረህ። ቀጥለህ ትንሣኤውንና ዕርገቱን ትሥላለህ። መጻሕፍት
በስንትና ስንት ምዕራፍ ያካተቱትን ታሪክ ሠዓሊው በጥቂት ብራናዎች አሣምሮ ቀምሮ ያስቀምጠዋል። ስለዚህ ምሥጢራቱን፣ የቱ ቀድሞ
የትኛው ሚከተል መሆኑን መመርመር ያስፈልጋል፤ የቀለም ማሳመር ብቻ ለሠዓሊነት አይበቃም።”
ጥላዬ፣ በተመስጦ አዳመጠና “እሺ የንታ፤ ንባቤንም ሥራዬንም
ተግቼ እቀጥላለሁ፤ ቃለ ሕይወት ያሰማልኝ” አላቸው፣ ትምህርታቸውን ከልቡ አዳምጦ።
“ዋናው ነገር እሱ ነው... ትጋት” አሉት፣ ሌባ ጣታቸውን እያወዛወዙ። “አንተን ትጉ ሁነህ አግኝቸኻለሁ። ምን ስጦታ ያለው ቢሆን ትጋት የሌለው ተማሪ አልወድም። ሥዕል ችሎታ ቢኖርህ ትጋት ኻላሳየህ ለሥራህ ጥሩ አይሆንም። አሁን በየቦታው ያሉት የተከበሩት ሠዓሊዎች አለሱ ሌላ ንሮ የላቸውም። አንዳንድ ተማሪ ይመጣል ኸኔ ዘንድ።እንዳው ብቻ ጫር ጫር አርጎ ቤተክሲያን ውስጥ ገብቶ ሥዕል
መሣል ይፈልጋል። ይኸ እንዴት ብሎ ይሆናል? ሥዕል ቀልድ ነው
እንዴ? እኔማ እንደዚያ ያለውን ተማሪ ኸኔ ዘንድ አላቆየውም። አንተ ለሥዕልም ለቤተክሲያንም አትሆንም ብየ ነው ምሰደው። ችሎታ አለ ትጋት ምንድርነው? አይምሰልህ ጥላዬ ሥራን ትልቅ ደረጃ ሚያደርሰው ትጋት ነው። እኔስ ብሆን አንድ ተማሪ ትጋት ካላሳየ ኸሱ ጋር ስለምን
እደክማለሁ? እስቲ በል ንገረኝ?”
“ውነት ነው... ውነት ነው” አለ፣ ጥላዬ ራሱን በአዎንታ እየነቀነቀ።
ልቡ ተነካ። ሥዕል እየሣለ ቤተክርስቲያንን ማገልገል እንዳለበት ይመኝ እንጂ፣ እንደዚህ ጠለቅ ብሎ ነገሩን አስቦበት አያውቅም።በአካባቢው የሚያያቸውን ቤቶች፣ ሰዎችና እንስሳት ቤታቸው ግድግዳ
ላይ ሲሥል ቢቆይም፣ የሚሥላቸውን ምስሎች ለዘላለም ቀርጾ ማስቀመጥ ከሚመኛቸው ነገሮች አንዱና ዋነኛው ምንትዋብን ነው። በተለይም
ደግሞ ነጠላ ተከናንባ ከቤተክርስቲያን ስትወጣ ያያት የነበረውን።
“ለሥዕል ያለኝ መውደድ ለብቻ ነው። ኸርሶ ዘንድ መማሬ ደሞ
ይበልጥ እንድወደው አድርጎኛል።”
“እኔም ለሥዕል ይኸ ነው ተብሎ ማይነገር ፍቅር አለኝ” አሉት።
“አለሱ ሌላ ሕይወት የለኝም። ሥዕል ሳይ እመራመራለሁ። የሠራሁትን ሥራ መልሼ ሳየው 'በውነት ይኸን የሠራኹ እኔ ነኝ ወይስ በኔ እጅ ራሱ ባለቤቱ ሣለው ብዬ እደነቃለኹ። ሥዕል የእዝጊሃር ወይም የደቂቀ
አማልክቱ ሥራ እንጂ የእኛ የደካሞቹ ፍጥረት አይመስለኝም። ጥላዬ...ሥዕል እኮ እንደ ቅኔ ከሳቴ ብርሃን ነው... የተደበቀውን ምሥጢር ሁሉ ሚገልጥ... ብርሃን ሚሰጥ። ለዝኽ ነው ቅኔን ብዙ ሊቃውንት ልሳነ መላእክት ነው ሚሉት።
ጥላዬ፣ መስማማቱን ለማሳየት ራሱን ነቀነቀ። “የንታ ሥዕል ለመማር እንደዛ ስመኝ ቆይቸ አሁን መማር በመቻሌ ዕድለኛ ሁኛለሁ።”
“ዕድል ኸሰማይ አይወድቅም” አሉት፣ ፊታቸውን ወደሱ መልሰው።
“ዕድል እንደ ሥዕል ነው። ሚገባው ዘንድ ነው ሚኸድ። ማይሆነው... ዝግጁ ሁኖ ማይጠብቀው ዘንድ አይኸድም። ወይም ማይሆነውን አይጣራም። ዕድል ልክ እንደ ሥዕል ሚፈልገውን ያውቃል፣ አውቆም
ይጣራል፣ ወይም ራሱ ወደሱ ይኸዳል። እንዳንተ ያለውን... የነፍሱን ጥሪ ሚያቀውን ኻለበት ፈልጎ ያወጣዋል። አንተም ዛዲያ ስትፈልገው፣ እሱም ሲፈልግህ... ስትፈላለጉ ቆይታችሁ ተገናኛችሁ።”
“አየ የንታ የእዝጊሃር ቸርነት ተጨምሮበት ነው።”
እዝጊሃር እኮ ማትችለውን አይሰጥህም። ጎበዝ ብትሆን ነው የሰጠህ።”
ውነት ነው አለ፣ ለራሱ።
“አሁን ይልቅ ምመክርህ” አሉት፣ ሌባ ጣታቸውን እያወዛወዙ፣ “ደብረ ወርቅ ኸደህ ሌሎች አስተማሮች ዘንድ መማርን ነው። እንደ ሌላው ትምርት ሁሉ ሥዕል እየተዘዋወርህ ስትማር ብዙ ትምርት ትቀስማለህ፣
ችሎታህንም ታዳብራለህ። ደብረ ወርቅ ታላላቅ የሥዕል መምህሮች
አሉ። እኔ እንደምታየው እያረዥሁ ነው። ኸንግዲህ እንደድሮው
ማስተማር አልችልም። አንተንም ገና ሳይህ ቀልቤ ስላረፈብህ
ተቀበልኩህ እንጂ ማስተማር እተዋለሁ እያልሁ ነበር” አሉት።
“የንታ ኸርሶ ዘንድ በቆየሁ። ኸርሶ መለየቱ ይከብደኛል።”
“ምን ይደረግ። እየደከመኝ መጣሁ።”
“ኸዝሁ ሌላ መምር ዘንድ ብቆይስ?”
“ሊቀጠበብት ኣዳሙ ዘንድ ነው እንድትማር የፈለግሁት። አዳሙ
ወደር ማይገኝለት መምህር ነው። ለኔም የረዥም ግዝየ ወዳጄ
ነው። እስታሁንም ብዙ ተማሮቸን ወደሱ ልኬያለሁ። አንተም ኸሱ
ዘንድ እንድትማር ነው ምፈልግ። ትምርትህን ስትጨርስ ተመልሰህ
ትመጣለህ።”
ጥላዬ፣ ጐንደር የዕድል በር ከፈተችልኝ፣ አለቃን መምህሬ፣ ጐንደርን ቤቴ ብሎ ተመቻችቶ ተቀምጦ፣ እንደዚህ ዓይነቱ ዱብ ዕዳ ሲመጣበት ደነገጠ፤ ሆድ ባሰው፤ መንፈሱ ተረበሸ፤ ተስፋ ሊቆርጥ ቃጣው።ከአለቃ ሔኖክ ሥር ሆኖ ታላቅ ሠዓሊ ለመሆን ያደረበትን ምኞት፣ከቤቱ ሲወጣ የሥዕል ንጉሥ ለመሆን የነበረውን ሕልም ሁሉ ጉም ሸፈነው። ደብረ ወርቅ ይሂድ ወይንም እዛው ጐንደር ሌላ አስተማሪ ዘንድ ይማር ለመወሰን አቃተው፤ ግራ ገባው። ምንትዋብን በአካል
ባያገኛትም እንኳ ከእሷ ርቆ መኖሩ ደግሞ አሳሰበው፣ አሳዘነው።....
።።።።።።።።።።፡፡።።።።።።።።።።።።
“ቁስቋም ብዙ ነገር ሰጥታኛለች፣ ወንድ ልዥ ደሞ ብትሰጠኝ።”
👍13😁1
አፄ በካፋ ሠራዊታቸው የሰፈረበት አሪንጎ ወይም የዕረፍት ቦታቸው ይባባ፣ አለበለዚያም ግብር አልከፍልም ያለውን ሊያስገብሩና
ወሰናቸውን ሊያስከብሩ በየቦታው ሲዘዋወሩ፣ ጣና አጠገብ ብርጊዳ
ገዳም ሲሄዱ፣ አደን ሲወጡ፣ እልፍኝ ገብተው ጉዳይ ሲፈጽሙ ወይም መሠሪ የተባለው ድብቅ ቦታ ገብተው ከመሣፍንትና ከመኳንንት ጋር ሲመክሩ፣ ምንትዋብና አያቷ ፋሲል ቤተመንግሥት አናት ላይ ያለው
ሰገነት ላይ ተያይዘው ይወጡና የቤተመንግሥቱን ዙርያ ገባውን
ይፈትሻሉ።
ሰገነቱ መላ ጐንደርንና ጣናን ከማሳየትም አልፎ፣ ወሬ ከሚለቅመውና ከሚያስፋፋው የቤተመንግሥት ባለሟል ጆሮ እርቀው ማውራት እንዲችሉ ይረዳቸዋል። ምንትዋብ ደግሞ ጠባቂዋ ከሆነውና በሄደችበት
እንደ ጭራ ከሚከተላት ጃንደረባ ራቅ ስለምትል ደስ ይላታል።
ከንድ ቀን እንደዚሁ ሰገነቱ ላይ ተቀምጠው ሲጫወቱ፣ “
እሚታዬ እኼን ጠዋት ላይ ሽቅብ ሚለኝን አልቻልሁትም። እስከመቸ ነው እንዲህ ሚተናነቀኝ?” ዐይኖቿን ጨፈን አድርጋ ወደ ኋላዋ ጋለል አለች።
“አይዞሽ እሱ ለግዝየው ነው፤ ይተውሻል። ብቻ ወንድ ያርግልሽ።
ጃንሆይም ቢሆኑ ይውደዱሽ እንጂ አይምሰልሽ አልጋ ወራሽ
ይፈልጋሉ።“
“ወንድ ሳልወልድ ብቀርስ?”
“ለቁስቋም ተይላት። ምን ግዝየም ቢሆን ከኛ ጋር ነች፤ አትጨነቂ።ይልቅስ... ያው... ቤተመንግሥት ወዳጅም ተቀናቃኝም ያለበት ማዶል? ማን ምን እንደሆነ ማወቁም ይጠቅማል” አሏት፣ ወሬውን
ለመለወጥ።
“እሚታዬ ትክክል ብለሻል። እንደምታውቂው” ብላ ጀመረች,
ወሬውን ስለቀየሩ ደስ ብሏት። “እንደምታውቂው ጃንሆይ ኸመሣፍነቱና ኸመኳንንቱ ጋር ምክር ሲይዙ እኔ አልገባም። ግና መሣፍንቱና መኳንንቱ ቤተመንግሥት መጥተው ኸሳቸው ጋር ሲጫወቱ አንዳንድ
ነገር አስተውላለሁ። አስተዋዮቹ እንዳይሰሙኝ” አለች፣ ወደ እንቁላል ግንቦቹ እያየች፣ ውስጥ የቆሙት ዘበኞች ይሰሙ እንደሆን ለማየት።
ስማቸውን ሳትጠራ፣ “እኛ” አለች፣ ዐይኗን ከወዲያ ወዲህ
አዘዋውራ፣ ልታወራ የፈለገችውን ሰውዬ በማስመሰል።
“እ... እ ገባኝ ማነን እንደምትይ።”
“አይገርምሽም? ነገራቸው ሁሉ ዙርያ።”
“እሳቸው ይቅር ላንቺ ለኛም ለትልልቆቹ ሰውን ጠንቅቀን እናውቃለን ለምንለው ግራ ናቸው።”
“እስቲ ፊታቸውን እዪ። አንድ ሰው አንድ ነገር ሲል ያነን የድመት
የመሰለ ዐይናቸውን ኸወዲያ ወዲህ ያቁለጨልጫሉ። ሰው ሚለውን በቅን ልቦና ማዳመጥ አይችሉ።”
ከዚያ በፊት እንደዛ ስትናገር ሰምተዋት አያውቁምና ተገረሙ። “ማን ነበር ስማቸው? እኛ ራሳቸው ገለጥ ያለው... እኛ ስንዝር ሚያህለት...?እኛ ማይጠዳቸው?”
“እሚታዬ ገብቶኛል ማነን እንደምትይ። ውነትሽን ነው፤ ፊታቸው አይፈታም። እሳቸው ዛዲያ ነገር ያሸንፋቸዋል ይባላል። ምላሳቸውም ብርቱ ነው። ኸኛ ቅድም ያልሁሽ... ኸሳቸው የባሱ ነገር ሽራቢ ናቸው።
ሁለቱ ደሞ ኩታና ቀሚስ ናቸው። ጃንሆይ ሁለቱንም አይወዱ። ሁለቱም ሚሉትን ከቁብም አያገቡ። ኸፈለጉ እኮ ኻገር ይነቅሏቸዋል። እንዳው
ችላ ብለዋቸው ነው እንጂ።”
“ልክ ነው።”
“እኝህ... ረዥሙ... ደጃማቹ... ደሞ አስመሳይ። ኸውስጥ ግን ኸኛ ኸጓደኛቸው... ገባሽ ማን እንደሆኑ?”
ዮልያና ራሳቸውን ነቀነቁላት ሰዎቹ ማን እንደሆኑ ማወቃቸውን
ለማመልከት። ብዙ ጊዜ አብረው ያይዋቸዋል።
“ዛዲያ ኸሳቸው ጋር ሚሸርቡት ያለ ይመስለኛል። ሁሌ ሺንሾኳሽሁ
ነው ማያቸው።”
“ሚዶልቱትን አያጡም። ወዳጅነት የገጠሙትም ለይሁ ይሆናል።
አሁን እየተረጋጋ መጣ እንጂ ጃንሆይ እንደነገሡ እኮ ብዙ አመጥ ነበር። ዛዲያ እኚ ረዥሙ በስንት አማላጅ ደሞም እግር ስመው ነው ጃንሆይ ይቅር ያሏቸው። እሳቸው ግና ኸውስጥ ሚጠነስሱት አያጡም።ያኔ ያመጡ ግዝየ ጃንሆይ ሌሎቹን እንደሚያረጉት እጃቸውን
ወይም እግራቸውን ያስቆርጧቸው አሊያም ያሰቅሏቸው ነበር። ብቻ
ኸመሣፍንቱና ኸመኳንንቱ ጋር መክረው ማሯቸው። እሳቸው ዛዲያ ይሉኝታ ባደረባቸው። ያነን ሁሉ መርበትበትና እግር መሳም ረስተው አሁንም አያርፉ፡፡”
“ከቤት እሚታዬ ጃንሆይ ግን እኼን እጅና እግር ሚያስቆርጡትን
ቢተዉ።”
“እንግዲህ...” አሉ፣ የሚሉት ጠፍቷቸው።
ገባትና ወሬውን ቀየረች። “እኛ ግጥሜ ናቸው ምልሽ የቅኔ ሊቁ...
እኛ ሁሌ ወዳቸዋለሁ ምልሽ... ምንም ውስጥ አይገቡ። ለጃንሆይም ታማኝ ናቸው” አለቻቸው።
“እሳቸው እኮ በትምርት የሰለጠኑ... ትምርታቸውንም ለመልካም ሚያውሉ ናቸው። እሳቸውና እኛ ጓደኛቸው ቄስ ገበዙ ምስጉን ሰዎች ናቸው። ለጃንሆይ ታማኝ ናቸው ላልሽው ታማኝነታቸው እኮ ለሳቸው
ማዶል፤ ለዘውዱ ነው። ዋናው እኮ ዘውዱ ነው። እሳቸውን ቢጠሉ
ስንኳ ለዘውዱ ታማኝ መሆን ይገባቸዋል። ንጉሦች እኮ ይመጣሉ፣ይኸዳሉ። ጥሩም ይመጣል፤ መጥፎም ይመጣል። ቀሪው... አገር አንድ ሚያረገው ዘውዱ ነው።”
በዝምታ ተቀመጡ።
ፈገግ አለችና፣ “እሚታዬ... እኔ መቸም አንድም ቀን ቤተመንግሥት ገባለሁ ብየ አስቤም አላውቅም። የት ብየ አስቤው? እዛው እቋራ
ላንዱ ትድሩኛላችሁ ብየ ነበር ማስብ እንጂ። መቸም ማን አሰበ
እኼን ሁሉ? አንቺ እንደዛ 'የተራ ባላባት ምሽትማ አትሆኚም' ስትይኝ ቤተመንግሥት ገባሁልሽ!” አለቻቸው።
“ያን ግዝየማ ቤተመንግሥት መግባት እንዴት ብለሽ ታስቢያለሽ? በያ ላይ ደሞ ሰው መቸም በሚኖርበት ልክ ነው ሚያስብ። ኻላየ...ኻላወቀ እንዴት ብሎ የሩቁን ያስባል? ለነገሩ እኔም ብሆን 'የተራ ባላባት ልዥ ምሽትማ አትሆኚም' ስልሽ መች ይኸን አስቤ! እንዲያው ቸሩ እዝጊሃር አንደበቴን ከፍቶ አናገረኝ! ግና ስንኳንም የኛን የሁነኝን
ልዥ አላገባሽ።”
ግንባሯ ተኮማተረ። “እሚታዬ ምን አረገ?”
“እኔ ኸልዥየው ጠብ የለኝም። አባትየው...”
“ያለፈ ነገር ነው። ስለሱ ማውራት ምን ያስፈልጋል?”
“የተራ ባላባት ልዥ ምሽትማ አትሆኚም አልሽኝ ብትይኝ ነዋ
ነገሩን ያነሳሁት።”በዝምታ ተቀመጡ።
እሷ ስለ አሁኑ ሕይወቷ ከሰማችበት ሰዐት ጀምሮ ታልመው የነበረው የሕይወት መንገድ አቅጣጫው መቀየሩ፣ ከጥላዬ... ከእዚያ የልጅነት
ፍቅሯ... ተራርቀው መኖራቸው ብቻ ሳይሆን፣ እሷ በወርቅ፣ በብር፣
ከፋርስ፣ ከህንድ፣ ከቱርክና ከየመን በመጣ ሐርና ምንጣፍ የተንቆጠቆጠ ቤተመንግሥት ውስጥ መኖሯ፣ ከካይሮ የመጣ ሐር መልበሷና ጊዜም ቢሆን ምንኛ ከዳተኛ መሆኑን መገንዘቧ ከንፈሯን አስመጠጣት፣ እንደ
መተከዝም አደረጋት። ከጥላዬም ጋር ቢሆን የሕይወታቸው ምዕራፍ
እንደተዘጋ አውቃ ባለበት ደሕና ይሁን፡፡ ቁስቋም እኼን ሁሉ ለኔ
እንደሰጠችኝ ለሱም ታስብለት አለችና ለአያቷ፣ “መቸም ዕድለኛ ነኝ”አለች።
“አንቺ ደሞ እናትሽን ይመስል ዕድል ዕድል ትያለሽ። ዕድል
ኸሰማይ ይወድቃል እንዴ? አታይም እንዴ አሁንስ ቢሆን ጃንሆይ ስላንቺ ያላቸውን ግምት? እንዳውስ ስላንቺ አውርተው ይጠግባሉ?እኼ ዕድል ነው በይኛ! ሚገባሽን ነው ያገኘሽው።”
“ቁስቋም ብዙ ነገር ሰጥታኛለች፣ ወንድ ልዥ ደሞ ብትሰጠኝ።”
“ትሰጥሻለች። ምን ይሳናታል? አሁን ስለሱ አታስቢ።”.....
✨ይቀጥላል✨
ወሰናቸውን ሊያስከብሩ በየቦታው ሲዘዋወሩ፣ ጣና አጠገብ ብርጊዳ
ገዳም ሲሄዱ፣ አደን ሲወጡ፣ እልፍኝ ገብተው ጉዳይ ሲፈጽሙ ወይም መሠሪ የተባለው ድብቅ ቦታ ገብተው ከመሣፍንትና ከመኳንንት ጋር ሲመክሩ፣ ምንትዋብና አያቷ ፋሲል ቤተመንግሥት አናት ላይ ያለው
ሰገነት ላይ ተያይዘው ይወጡና የቤተመንግሥቱን ዙርያ ገባውን
ይፈትሻሉ።
ሰገነቱ መላ ጐንደርንና ጣናን ከማሳየትም አልፎ፣ ወሬ ከሚለቅመውና ከሚያስፋፋው የቤተመንግሥት ባለሟል ጆሮ እርቀው ማውራት እንዲችሉ ይረዳቸዋል። ምንትዋብ ደግሞ ጠባቂዋ ከሆነውና በሄደችበት
እንደ ጭራ ከሚከተላት ጃንደረባ ራቅ ስለምትል ደስ ይላታል።
ከንድ ቀን እንደዚሁ ሰገነቱ ላይ ተቀምጠው ሲጫወቱ፣ “
እሚታዬ እኼን ጠዋት ላይ ሽቅብ ሚለኝን አልቻልሁትም። እስከመቸ ነው እንዲህ ሚተናነቀኝ?” ዐይኖቿን ጨፈን አድርጋ ወደ ኋላዋ ጋለል አለች።
“አይዞሽ እሱ ለግዝየው ነው፤ ይተውሻል። ብቻ ወንድ ያርግልሽ።
ጃንሆይም ቢሆኑ ይውደዱሽ እንጂ አይምሰልሽ አልጋ ወራሽ
ይፈልጋሉ።“
“ወንድ ሳልወልድ ብቀርስ?”
“ለቁስቋም ተይላት። ምን ግዝየም ቢሆን ከኛ ጋር ነች፤ አትጨነቂ።ይልቅስ... ያው... ቤተመንግሥት ወዳጅም ተቀናቃኝም ያለበት ማዶል? ማን ምን እንደሆነ ማወቁም ይጠቅማል” አሏት፣ ወሬውን
ለመለወጥ።
“እሚታዬ ትክክል ብለሻል። እንደምታውቂው” ብላ ጀመረች,
ወሬውን ስለቀየሩ ደስ ብሏት። “እንደምታውቂው ጃንሆይ ኸመሣፍነቱና ኸመኳንንቱ ጋር ምክር ሲይዙ እኔ አልገባም። ግና መሣፍንቱና መኳንንቱ ቤተመንግሥት መጥተው ኸሳቸው ጋር ሲጫወቱ አንዳንድ
ነገር አስተውላለሁ። አስተዋዮቹ እንዳይሰሙኝ” አለች፣ ወደ እንቁላል ግንቦቹ እያየች፣ ውስጥ የቆሙት ዘበኞች ይሰሙ እንደሆን ለማየት።
ስማቸውን ሳትጠራ፣ “እኛ” አለች፣ ዐይኗን ከወዲያ ወዲህ
አዘዋውራ፣ ልታወራ የፈለገችውን ሰውዬ በማስመሰል።
“እ... እ ገባኝ ማነን እንደምትይ።”
“አይገርምሽም? ነገራቸው ሁሉ ዙርያ።”
“እሳቸው ይቅር ላንቺ ለኛም ለትልልቆቹ ሰውን ጠንቅቀን እናውቃለን ለምንለው ግራ ናቸው።”
“እስቲ ፊታቸውን እዪ። አንድ ሰው አንድ ነገር ሲል ያነን የድመት
የመሰለ ዐይናቸውን ኸወዲያ ወዲህ ያቁለጨልጫሉ። ሰው ሚለውን በቅን ልቦና ማዳመጥ አይችሉ።”
ከዚያ በፊት እንደዛ ስትናገር ሰምተዋት አያውቁምና ተገረሙ። “ማን ነበር ስማቸው? እኛ ራሳቸው ገለጥ ያለው... እኛ ስንዝር ሚያህለት...?እኛ ማይጠዳቸው?”
“እሚታዬ ገብቶኛል ማነን እንደምትይ። ውነትሽን ነው፤ ፊታቸው አይፈታም። እሳቸው ዛዲያ ነገር ያሸንፋቸዋል ይባላል። ምላሳቸውም ብርቱ ነው። ኸኛ ቅድም ያልሁሽ... ኸሳቸው የባሱ ነገር ሽራቢ ናቸው።
ሁለቱ ደሞ ኩታና ቀሚስ ናቸው። ጃንሆይ ሁለቱንም አይወዱ። ሁለቱም ሚሉትን ከቁብም አያገቡ። ኸፈለጉ እኮ ኻገር ይነቅሏቸዋል። እንዳው
ችላ ብለዋቸው ነው እንጂ።”
“ልክ ነው።”
“እኝህ... ረዥሙ... ደጃማቹ... ደሞ አስመሳይ። ኸውስጥ ግን ኸኛ ኸጓደኛቸው... ገባሽ ማን እንደሆኑ?”
ዮልያና ራሳቸውን ነቀነቁላት ሰዎቹ ማን እንደሆኑ ማወቃቸውን
ለማመልከት። ብዙ ጊዜ አብረው ያይዋቸዋል።
“ዛዲያ ኸሳቸው ጋር ሚሸርቡት ያለ ይመስለኛል። ሁሌ ሺንሾኳሽሁ
ነው ማያቸው።”
“ሚዶልቱትን አያጡም። ወዳጅነት የገጠሙትም ለይሁ ይሆናል።
አሁን እየተረጋጋ መጣ እንጂ ጃንሆይ እንደነገሡ እኮ ብዙ አመጥ ነበር። ዛዲያ እኚ ረዥሙ በስንት አማላጅ ደሞም እግር ስመው ነው ጃንሆይ ይቅር ያሏቸው። እሳቸው ግና ኸውስጥ ሚጠነስሱት አያጡም።ያኔ ያመጡ ግዝየ ጃንሆይ ሌሎቹን እንደሚያረጉት እጃቸውን
ወይም እግራቸውን ያስቆርጧቸው አሊያም ያሰቅሏቸው ነበር። ብቻ
ኸመሣፍንቱና ኸመኳንንቱ ጋር መክረው ማሯቸው። እሳቸው ዛዲያ ይሉኝታ ባደረባቸው። ያነን ሁሉ መርበትበትና እግር መሳም ረስተው አሁንም አያርፉ፡፡”
“ከቤት እሚታዬ ጃንሆይ ግን እኼን እጅና እግር ሚያስቆርጡትን
ቢተዉ።”
“እንግዲህ...” አሉ፣ የሚሉት ጠፍቷቸው።
ገባትና ወሬውን ቀየረች። “እኛ ግጥሜ ናቸው ምልሽ የቅኔ ሊቁ...
እኛ ሁሌ ወዳቸዋለሁ ምልሽ... ምንም ውስጥ አይገቡ። ለጃንሆይም ታማኝ ናቸው” አለቻቸው።
“እሳቸው እኮ በትምርት የሰለጠኑ... ትምርታቸውንም ለመልካም ሚያውሉ ናቸው። እሳቸውና እኛ ጓደኛቸው ቄስ ገበዙ ምስጉን ሰዎች ናቸው። ለጃንሆይ ታማኝ ናቸው ላልሽው ታማኝነታቸው እኮ ለሳቸው
ማዶል፤ ለዘውዱ ነው። ዋናው እኮ ዘውዱ ነው። እሳቸውን ቢጠሉ
ስንኳ ለዘውዱ ታማኝ መሆን ይገባቸዋል። ንጉሦች እኮ ይመጣሉ፣ይኸዳሉ። ጥሩም ይመጣል፤ መጥፎም ይመጣል። ቀሪው... አገር አንድ ሚያረገው ዘውዱ ነው።”
በዝምታ ተቀመጡ።
ፈገግ አለችና፣ “እሚታዬ... እኔ መቸም አንድም ቀን ቤተመንግሥት ገባለሁ ብየ አስቤም አላውቅም። የት ብየ አስቤው? እዛው እቋራ
ላንዱ ትድሩኛላችሁ ብየ ነበር ማስብ እንጂ። መቸም ማን አሰበ
እኼን ሁሉ? አንቺ እንደዛ 'የተራ ባላባት ምሽትማ አትሆኚም' ስትይኝ ቤተመንግሥት ገባሁልሽ!” አለቻቸው።
“ያን ግዝየማ ቤተመንግሥት መግባት እንዴት ብለሽ ታስቢያለሽ? በያ ላይ ደሞ ሰው መቸም በሚኖርበት ልክ ነው ሚያስብ። ኻላየ...ኻላወቀ እንዴት ብሎ የሩቁን ያስባል? ለነገሩ እኔም ብሆን 'የተራ ባላባት ልዥ ምሽትማ አትሆኚም' ስልሽ መች ይኸን አስቤ! እንዲያው ቸሩ እዝጊሃር አንደበቴን ከፍቶ አናገረኝ! ግና ስንኳንም የኛን የሁነኝን
ልዥ አላገባሽ።”
ግንባሯ ተኮማተረ። “እሚታዬ ምን አረገ?”
“እኔ ኸልዥየው ጠብ የለኝም። አባትየው...”
“ያለፈ ነገር ነው። ስለሱ ማውራት ምን ያስፈልጋል?”
“የተራ ባላባት ልዥ ምሽትማ አትሆኚም አልሽኝ ብትይኝ ነዋ
ነገሩን ያነሳሁት።”በዝምታ ተቀመጡ።
እሷ ስለ አሁኑ ሕይወቷ ከሰማችበት ሰዐት ጀምሮ ታልመው የነበረው የሕይወት መንገድ አቅጣጫው መቀየሩ፣ ከጥላዬ... ከእዚያ የልጅነት
ፍቅሯ... ተራርቀው መኖራቸው ብቻ ሳይሆን፣ እሷ በወርቅ፣ በብር፣
ከፋርስ፣ ከህንድ፣ ከቱርክና ከየመን በመጣ ሐርና ምንጣፍ የተንቆጠቆጠ ቤተመንግሥት ውስጥ መኖሯ፣ ከካይሮ የመጣ ሐር መልበሷና ጊዜም ቢሆን ምንኛ ከዳተኛ መሆኑን መገንዘቧ ከንፈሯን አስመጠጣት፣ እንደ
መተከዝም አደረጋት። ከጥላዬም ጋር ቢሆን የሕይወታቸው ምዕራፍ
እንደተዘጋ አውቃ ባለበት ደሕና ይሁን፡፡ ቁስቋም እኼን ሁሉ ለኔ
እንደሰጠችኝ ለሱም ታስብለት አለችና ለአያቷ፣ “መቸም ዕድለኛ ነኝ”አለች።
“አንቺ ደሞ እናትሽን ይመስል ዕድል ዕድል ትያለሽ። ዕድል
ኸሰማይ ይወድቃል እንዴ? አታይም እንዴ አሁንስ ቢሆን ጃንሆይ ስላንቺ ያላቸውን ግምት? እንዳውስ ስላንቺ አውርተው ይጠግባሉ?እኼ ዕድል ነው በይኛ! ሚገባሽን ነው ያገኘሽው።”
“ቁስቋም ብዙ ነገር ሰጥታኛለች፣ ወንድ ልዥ ደሞ ብትሰጠኝ።”
“ትሰጥሻለች። ምን ይሳናታል? አሁን ስለሱ አታስቢ።”.....
✨ይቀጥላል✨
👍19
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....አንዳንዴ የጊዜ ማጠርና መርዘም በሰዎች የውስጥ ስሜት የሚለካ ይመስላል ለተጨነቀ ልብና መንፈስ አንዱ አመት በአስራ ቤት የሚቆጠር ሲመስል ለተደሰተ ደግሞ የአንድ ቀን ያህል አጭር ይሆናል እሱ ግን አሁንም ኡደቱን ሳያዛባ እየሄደ ነው። እየነጎደ ነው።የቀንና የለሊት ፍርርቅ መሰረት አድርጎ ሳምንቱን በሳምንት ወሩንም በወር እየተካ ተምዘገዘገ። ብሎ ብሎ አንድ አመት አለቀና ሌላው ተጋመሰ
እነሆ አስቻለው አስመራ ከሄደ ሁለት ዓመት ከሶስት ወሩ! ሔዋን ክበረ መንግስት ከሄደች እንኳ አንድ ዓመት ከአራት ወር ሞላት። ሔዋን በክብረ መንግስት ታፈሡ በልሁና መርዕድ ዲላ ውስጥ እየኖሩ ይህ ጊዜ ከአስቻለው ትዝታና ናፍቆት ጋር በተያያዘ በተመሳሳይ የስሜት አቆጣጠር
እያሰቡት በመከራና በስቃይ ነው ያሳለፉት። አዝግሞ፣ ተጎትቶና ተንፏቆ ነው እዚህ የደረሰው። አንድ ክፍለ ዘመን ያህል ርቆባቸዋል። ለመምህርት ሸዋዬ ደግሞ በሚያስገርም ሁኔታ አጅግ አጭር ነበር።
ሸዋዬ በአስቻለውና በሔዋን መለያየት ቀድሞ የነበረባት የመንፈስ ቁስልወደ መገረን ተቀይሮ ከቅናት ስቃይ እፎይ ብላለች፡፡ ዛሬ የሁለቱ ፍቅር የዕለት
ተዕለት ሃሳብና ጭንቋ አይደለምና ፀሎቷ በዚሁ እንዲቀጥል ብቻ ነው። በሰላም የህይወት አጋጣሚ ውስጥ ገብታለች። ኑሮዋ ሞቅ ደመቅ እያለ ነው፡፡ ማህበራዊ ግንኙነቷም እየተሻሻለ ነው፡፡ ነቃ ነቃ ብላለች። የመንፈስ መረጋጋትም ይታይባታል። የአሁኑ ይዞታዋ ዘለቄታ እንዲኖረው ደፋ ቀና ማለቷን ተያይዛዋለች።
ለዚህ ሁሉ ሰበቡ የእናቷ ከክብረ መንግስት መምጣትና በአጭር ጊዜ ውስጥ ሔዋንን ይዘው ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ነበር። ያ አጋጣሚ በወቅቱ የእግር እሳት ሆኖ አንገብግቧት የነበረ ቢሆንም ለዛሬው ህይወቷ መሰረት ጥሉላት
ያለፈ በመሆኑ ግን በመልካም አጋጣሚነቱ እያስታወሰችው ትኖራለች።
የሔዋን እናት በሽዋዩ ቤት አድረው በነጋታው ወደ ሔዋን ጋ ከሄዱ በኋላ ከሸዋዬ ጋር ዳግም ሳይገናኙ ነበር ወደ ክብረ መንግስት የተመለሱት። በእርግጥ
መሄዴ ነውና ደህና ሁኚ' ሊሏት ከመሄዳቸው አንድ ቀን በፊት ወደ ቤቷ ጎራ ብለው ነበር፡፡ ግን አላገኟትም፡፡ ዕለቱ ባርናባስ ወየሶ በአንድ የሶሻሊስት አገር የውጭ ትምህርት ዕድል አግኝቶ ሊሄድ ሞቅ ደመቅ ባለ ድግስ የሚሸኝበት ቀን ነበርና ሸዋዬም የድግሱ ታዳሚ በመሆን ከድግሱ ቦታ አምሽታለች። የሔዋን እናት
ቶሎ የምትመለስ መስሏቸው ከወይዘሮ ዘነቡ ጋር እያወሩና እየተጫወቱ ቢጠብቋት
ቢቆዩም እሷ ግን እስከ ምሽት ድረስ ስለቆየችባቸው መልዕክቱ በወይዘሮ ዘነቡ በኩል እንዲደርሳት አድርገው ተመልሰዋል፡፡
ሽዋዬ የእናቷን ፈጥነው ወደ ክብረ መንግስት የመመለስ ጉዳይ ፈጽሞ ያሰበችው አልነበረም፡፡ በእሷ ግምት የሚሰነሳብቱና በዚያም አጋጣሚ የእሷንና
የሑዋንን ለየብቻ የመኖር ምክንያት ዋሽታም ቢሆን ቀጥፋ እውነታውን በመሽፈን
ልታወራላቸውና ራሷን ከተጠያቂነት ለማዳን የሚያስችሉ ብዙ መንገዶችን ፈጥራ ነበር፡፡ ግን ያ ካለመሆኑም በተጨማሪ እናቷ ከታፈሠ ጋር ውለው አድረው
እንዲሁም ከወይዘሮ ዘነቡ ጋር ብዙ ተጫውተው የመመለሳቸው ነገር ክፉኛ ነበር ያስደነገጣት፡፡ እነዚህ ሁለት ሰዎች የአስቻለውንና የሔዋንን ግንኙነት እንዲሁም እሷ በሁለቱ ፍቅረኛሞች ላይ የነበራትን አቋም እንዴት አድርገው ለእናቷ እንደሚገልጹላት ታውቃለችና በተፈጠረባት መጥፎ
አጋጣሚም እጅጉን ተበሳጭታም ተናድዳም ነበር፡፡
የእናቷን ወደ ክብረ መንግስት መመለስ ጉዳይ በስማችበት ወቅት የነበራት ምርጫ አንድ ብቻ ነበር። የጉዟውን ሁኔታ ታውቃለች፡፡ ዲላ ተነስተው በአለታ ወንዶ በኩል ነው የሚጓዙት። አለታ ወንዶ ሲደርሱ ከዲላ መኪና ላይ ወርደው ከአዲስ አበባ ወደ ክብረ መንግስት የሚሄደውን አውቶብስ መጠበቅ አለባቸው፡፡
በመሀል ቢያንስ ለሁለት ወይም ለሶስት ሰዓት ያህል አለታ ወንዶ ከተማ ይቆያሉ እናም ጠዋት ከዲላ ከተማ ተነስታ አብራቸው በመጓዝ አለታ ወንዶ
እስክሚደርሰብት ጊዜና በአለታ ወንዶ ከተማ በሚያደርጉት የቆይታ ጊዜ ውስጥ በወሬ ስትተከትካቸው ለመቆየት አስባ ይህንኑ ለመፈጸም ወስና አደረች::
በማግስቱ በጠዋት ተነሳች፡፡ እናቷን መሸንገያ የሚሆን ጥቂት ገንዘብ ቋጠረች። ወደ መናኸሪያው ገሰገሰች፡፡ ከእናቷ በፊት ቀድማ ከቦታው ደረሰች::
ሔዋን ከምትኖርበት አቅጣጫ ወደ መናኸሪያው በሚያመጣው መንገድ በርቀት ስትመለከት ስድስት ሰዎች ሲወጠ ታዩዋት። እየቀረቧት ሲሄዱ ማንነታቸውን
ለየች፡፡ እናቷ፥ ታፈሡ! በልሁ! መርዕድ፤ሔዋንና ትርፌ ናቸው፡፡ ዘንግታው እንጂ! ለካ እናቷ
መሸኘት ነበረባቸው:: ከተሸኙም በእነዚሁ ሰዎች ነው::ተበሳጨች፡፡ ከእናቷ ጋር በአንድ መኪና የመሳፈር ዕቅዷን ሰርዛ በተከታዩ ሎንችን ልትጓዝና እናቷን በአለታ ወንዶ ልትደርስባቸው፣ እዚያ በሚያደርጉት የቆይታ ጊዜ ብቻ ልታነጋግራቸውም ወሰነች፡፡ ለጊዜው በመናኻሪያው ውስጥ እንዳትታይ ወደ አንድ ሰዋራ ቦታ በመቆም የእናቷንና የሸኝዎቻቸውን እንቅስቃሴ መከታተል ጀመረች።
አሁንም የአላሰበችው ሁኔታ ተከሰተ፡፡ እሷ የምትጠብቀው የእናቷን መሄድ ብቻ ነበር፡፡ ግን ደግሞ ሔዋንም መኪና ላይ ወጥታ በመስኮት አንገትና እጇቿን
አውጥታ አፏን ቧ እድርጋ ከፍታ ምርር ብላ ስታለቅስና እጆቿን እያርገበገበች ታፈሡን ስትሰናበት አየች:: እነሱም አስከሬን ወደ ቀብር ቦታ ሸኝተው የሚመለሱ
ሀዘንተኞችን ያህል ምርር ብለው ሲያለቅሱና እጀቻቸውን እያርገበገቡ ሲሰናበቷት አየች።
«እንዴ! እሷም ልትሄድ!» አለች ሽዋዬ ለብቻዋ እየተነጋገረች። ገረማትም ደነቃትም:: ግን ለዕለቱ እቅዷ ምንም ዓይነት እንቅፋት እንደማይፈጥርባት ገመተች፣ እሷ ለእናቷ ስለሆነ ነገር ብታወራ በትዝብት ታዳምጥ እንደሆነ እንጂ
ሔዋን ደፍራ ክርክር እንደማትገጥማት ታውቃታለችና።
እነ ሔዋንና እናቷ በአለታ ወንዶ በኩል በሚሄደው አውቶብስ ተሳፍረው ከሄዱና ሽኝዎቻቸውም ከመናኸሪያው ወጥተው ወደየአቅጣጫቸው ከተበታተኑ በኋላ ሸዋዬ በቀጣይ ወደ አለታ ወንዶ የሚሄደውን መኪና ፍለጋ ጀመረች:: በእርግጥም
አንድ የመኪና ላይ ሰራተኛ የአንዲት አነስተኛ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በር
ከፍቶ «ወንዶ! ወንዶ! አለታ ወንዶ!» የሚል ጥሪ አሰማ። ሽዋዬ ወደ መኪናዋ ሮጣ
በመግባት የጋቢና ወንበር ይዛ ቁጭ አለች፡፡
ከአንድ ሠዓት አለፍ አለ፡፡ ያቺ መኪና ግን ቶሎ አልሞላ አለች፡፡ በዚያው ልክ ሸዋዬ ተበሳጨች ቸኩላ ጋቢና ወስጥ ቁጭ ብላ ፊትለፊት ስትመለከት በርካታ መንገደኛ ወደ መናኸሪያው ሲገባ ታያለኝ። ግን እሷ ወዴለችባት መኪና የሚገባው ሰው ከቁጥር አይገባም፡፡ ረዳቱ አሁንም "ወንዶ ወንዶ" እያለ መንገደኛ ይጠራል
ሸዋዬ ወደ ኋላ ዞር ብላ ስታይ ግን በርካታ ወንበሮች ክፍት ሆነው
ትመለከታለች: በዚያው ልክ ቀልቧ እየቆመ ትቁነጠነጥ ጀመር፡፡
ከመኪናዋ ወንበሮች ግማሽ ያህሉ በሰው ከተያዙ በኋላ ሹፌሩ ወደ መኪናዋ ገብቶ ሞተር አስነሳ፡፡ ነገር ግን ሞቅ ሞቅ ከአደረገ በኃላ ተመልሶ ሊወርድ ሲዘጋጅ ሸዋዬ አየችውና «በእናትህ ሾፌር መንገድ ላይ ትሞላለህ፥ እንሂድ» አለችው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....አንዳንዴ የጊዜ ማጠርና መርዘም በሰዎች የውስጥ ስሜት የሚለካ ይመስላል ለተጨነቀ ልብና መንፈስ አንዱ አመት በአስራ ቤት የሚቆጠር ሲመስል ለተደሰተ ደግሞ የአንድ ቀን ያህል አጭር ይሆናል እሱ ግን አሁንም ኡደቱን ሳያዛባ እየሄደ ነው። እየነጎደ ነው።የቀንና የለሊት ፍርርቅ መሰረት አድርጎ ሳምንቱን በሳምንት ወሩንም በወር እየተካ ተምዘገዘገ። ብሎ ብሎ አንድ አመት አለቀና ሌላው ተጋመሰ
እነሆ አስቻለው አስመራ ከሄደ ሁለት ዓመት ከሶስት ወሩ! ሔዋን ክበረ መንግስት ከሄደች እንኳ አንድ ዓመት ከአራት ወር ሞላት። ሔዋን በክብረ መንግስት ታፈሡ በልሁና መርዕድ ዲላ ውስጥ እየኖሩ ይህ ጊዜ ከአስቻለው ትዝታና ናፍቆት ጋር በተያያዘ በተመሳሳይ የስሜት አቆጣጠር
እያሰቡት በመከራና በስቃይ ነው ያሳለፉት። አዝግሞ፣ ተጎትቶና ተንፏቆ ነው እዚህ የደረሰው። አንድ ክፍለ ዘመን ያህል ርቆባቸዋል። ለመምህርት ሸዋዬ ደግሞ በሚያስገርም ሁኔታ አጅግ አጭር ነበር።
ሸዋዬ በአስቻለውና በሔዋን መለያየት ቀድሞ የነበረባት የመንፈስ ቁስልወደ መገረን ተቀይሮ ከቅናት ስቃይ እፎይ ብላለች፡፡ ዛሬ የሁለቱ ፍቅር የዕለት
ተዕለት ሃሳብና ጭንቋ አይደለምና ፀሎቷ በዚሁ እንዲቀጥል ብቻ ነው። በሰላም የህይወት አጋጣሚ ውስጥ ገብታለች። ኑሮዋ ሞቅ ደመቅ እያለ ነው፡፡ ማህበራዊ ግንኙነቷም እየተሻሻለ ነው፡፡ ነቃ ነቃ ብላለች። የመንፈስ መረጋጋትም ይታይባታል። የአሁኑ ይዞታዋ ዘለቄታ እንዲኖረው ደፋ ቀና ማለቷን ተያይዛዋለች።
ለዚህ ሁሉ ሰበቡ የእናቷ ከክብረ መንግስት መምጣትና በአጭር ጊዜ ውስጥ ሔዋንን ይዘው ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ነበር። ያ አጋጣሚ በወቅቱ የእግር እሳት ሆኖ አንገብግቧት የነበረ ቢሆንም ለዛሬው ህይወቷ መሰረት ጥሉላት
ያለፈ በመሆኑ ግን በመልካም አጋጣሚነቱ እያስታወሰችው ትኖራለች።
የሔዋን እናት በሽዋዩ ቤት አድረው በነጋታው ወደ ሔዋን ጋ ከሄዱ በኋላ ከሸዋዬ ጋር ዳግም ሳይገናኙ ነበር ወደ ክብረ መንግስት የተመለሱት። በእርግጥ
መሄዴ ነውና ደህና ሁኚ' ሊሏት ከመሄዳቸው አንድ ቀን በፊት ወደ ቤቷ ጎራ ብለው ነበር፡፡ ግን አላገኟትም፡፡ ዕለቱ ባርናባስ ወየሶ በአንድ የሶሻሊስት አገር የውጭ ትምህርት ዕድል አግኝቶ ሊሄድ ሞቅ ደመቅ ባለ ድግስ የሚሸኝበት ቀን ነበርና ሸዋዬም የድግሱ ታዳሚ በመሆን ከድግሱ ቦታ አምሽታለች። የሔዋን እናት
ቶሎ የምትመለስ መስሏቸው ከወይዘሮ ዘነቡ ጋር እያወሩና እየተጫወቱ ቢጠብቋት
ቢቆዩም እሷ ግን እስከ ምሽት ድረስ ስለቆየችባቸው መልዕክቱ በወይዘሮ ዘነቡ በኩል እንዲደርሳት አድርገው ተመልሰዋል፡፡
ሽዋዬ የእናቷን ፈጥነው ወደ ክብረ መንግስት የመመለስ ጉዳይ ፈጽሞ ያሰበችው አልነበረም፡፡ በእሷ ግምት የሚሰነሳብቱና በዚያም አጋጣሚ የእሷንና
የሑዋንን ለየብቻ የመኖር ምክንያት ዋሽታም ቢሆን ቀጥፋ እውነታውን በመሽፈን
ልታወራላቸውና ራሷን ከተጠያቂነት ለማዳን የሚያስችሉ ብዙ መንገዶችን ፈጥራ ነበር፡፡ ግን ያ ካለመሆኑም በተጨማሪ እናቷ ከታፈሠ ጋር ውለው አድረው
እንዲሁም ከወይዘሮ ዘነቡ ጋር ብዙ ተጫውተው የመመለሳቸው ነገር ክፉኛ ነበር ያስደነገጣት፡፡ እነዚህ ሁለት ሰዎች የአስቻለውንና የሔዋንን ግንኙነት እንዲሁም እሷ በሁለቱ ፍቅረኛሞች ላይ የነበራትን አቋም እንዴት አድርገው ለእናቷ እንደሚገልጹላት ታውቃለችና በተፈጠረባት መጥፎ
አጋጣሚም እጅጉን ተበሳጭታም ተናድዳም ነበር፡፡
የእናቷን ወደ ክብረ መንግስት መመለስ ጉዳይ በስማችበት ወቅት የነበራት ምርጫ አንድ ብቻ ነበር። የጉዟውን ሁኔታ ታውቃለች፡፡ ዲላ ተነስተው በአለታ ወንዶ በኩል ነው የሚጓዙት። አለታ ወንዶ ሲደርሱ ከዲላ መኪና ላይ ወርደው ከአዲስ አበባ ወደ ክብረ መንግስት የሚሄደውን አውቶብስ መጠበቅ አለባቸው፡፡
በመሀል ቢያንስ ለሁለት ወይም ለሶስት ሰዓት ያህል አለታ ወንዶ ከተማ ይቆያሉ እናም ጠዋት ከዲላ ከተማ ተነስታ አብራቸው በመጓዝ አለታ ወንዶ
እስክሚደርሰብት ጊዜና በአለታ ወንዶ ከተማ በሚያደርጉት የቆይታ ጊዜ ውስጥ በወሬ ስትተከትካቸው ለመቆየት አስባ ይህንኑ ለመፈጸም ወስና አደረች::
በማግስቱ በጠዋት ተነሳች፡፡ እናቷን መሸንገያ የሚሆን ጥቂት ገንዘብ ቋጠረች። ወደ መናኸሪያው ገሰገሰች፡፡ ከእናቷ በፊት ቀድማ ከቦታው ደረሰች::
ሔዋን ከምትኖርበት አቅጣጫ ወደ መናኸሪያው በሚያመጣው መንገድ በርቀት ስትመለከት ስድስት ሰዎች ሲወጠ ታዩዋት። እየቀረቧት ሲሄዱ ማንነታቸውን
ለየች፡፡ እናቷ፥ ታፈሡ! በልሁ! መርዕድ፤ሔዋንና ትርፌ ናቸው፡፡ ዘንግታው እንጂ! ለካ እናቷ
መሸኘት ነበረባቸው:: ከተሸኙም በእነዚሁ ሰዎች ነው::ተበሳጨች፡፡ ከእናቷ ጋር በአንድ መኪና የመሳፈር ዕቅዷን ሰርዛ በተከታዩ ሎንችን ልትጓዝና እናቷን በአለታ ወንዶ ልትደርስባቸው፣ እዚያ በሚያደርጉት የቆይታ ጊዜ ብቻ ልታነጋግራቸውም ወሰነች፡፡ ለጊዜው በመናኻሪያው ውስጥ እንዳትታይ ወደ አንድ ሰዋራ ቦታ በመቆም የእናቷንና የሸኝዎቻቸውን እንቅስቃሴ መከታተል ጀመረች።
አሁንም የአላሰበችው ሁኔታ ተከሰተ፡፡ እሷ የምትጠብቀው የእናቷን መሄድ ብቻ ነበር፡፡ ግን ደግሞ ሔዋንም መኪና ላይ ወጥታ በመስኮት አንገትና እጇቿን
አውጥታ አፏን ቧ እድርጋ ከፍታ ምርር ብላ ስታለቅስና እጆቿን እያርገበገበች ታፈሡን ስትሰናበት አየች:: እነሱም አስከሬን ወደ ቀብር ቦታ ሸኝተው የሚመለሱ
ሀዘንተኞችን ያህል ምርር ብለው ሲያለቅሱና እጀቻቸውን እያርገበገቡ ሲሰናበቷት አየች።
«እንዴ! እሷም ልትሄድ!» አለች ሽዋዬ ለብቻዋ እየተነጋገረች። ገረማትም ደነቃትም:: ግን ለዕለቱ እቅዷ ምንም ዓይነት እንቅፋት እንደማይፈጥርባት ገመተች፣ እሷ ለእናቷ ስለሆነ ነገር ብታወራ በትዝብት ታዳምጥ እንደሆነ እንጂ
ሔዋን ደፍራ ክርክር እንደማትገጥማት ታውቃታለችና።
እነ ሔዋንና እናቷ በአለታ ወንዶ በኩል በሚሄደው አውቶብስ ተሳፍረው ከሄዱና ሽኝዎቻቸውም ከመናኸሪያው ወጥተው ወደየአቅጣጫቸው ከተበታተኑ በኋላ ሸዋዬ በቀጣይ ወደ አለታ ወንዶ የሚሄደውን መኪና ፍለጋ ጀመረች:: በእርግጥም
አንድ የመኪና ላይ ሰራተኛ የአንዲት አነስተኛ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በር
ከፍቶ «ወንዶ! ወንዶ! አለታ ወንዶ!» የሚል ጥሪ አሰማ። ሽዋዬ ወደ መኪናዋ ሮጣ
በመግባት የጋቢና ወንበር ይዛ ቁጭ አለች፡፡
ከአንድ ሠዓት አለፍ አለ፡፡ ያቺ መኪና ግን ቶሎ አልሞላ አለች፡፡ በዚያው ልክ ሸዋዬ ተበሳጨች ቸኩላ ጋቢና ወስጥ ቁጭ ብላ ፊትለፊት ስትመለከት በርካታ መንገደኛ ወደ መናኸሪያው ሲገባ ታያለኝ። ግን እሷ ወዴለችባት መኪና የሚገባው ሰው ከቁጥር አይገባም፡፡ ረዳቱ አሁንም "ወንዶ ወንዶ" እያለ መንገደኛ ይጠራል
ሸዋዬ ወደ ኋላ ዞር ብላ ስታይ ግን በርካታ ወንበሮች ክፍት ሆነው
ትመለከታለች: በዚያው ልክ ቀልቧ እየቆመ ትቁነጠነጥ ጀመር፡፡
ከመኪናዋ ወንበሮች ግማሽ ያህሉ በሰው ከተያዙ በኋላ ሹፌሩ ወደ መኪናዋ ገብቶ ሞተር አስነሳ፡፡ ነገር ግን ሞቅ ሞቅ ከአደረገ በኃላ ተመልሶ ሊወርድ ሲዘጋጅ ሸዋዬ አየችውና «በእናትህ ሾፌር መንገድ ላይ ትሞላለህ፥ እንሂድ» አለችው፡፡
👍6👏1
እንሄዳለን፡፡ አላትና ከመኪናው ላይ ወረደ:: ቁልፎቹን እያቅጨለጨለ
በመኪናዋ አካባቢ ይንጎራደድ ጀመር።
ሾፌሩ ጥቁርና ጠብሰቅ ያለ ሰውነት ያለው ነው: ቁመቱዎ ዘለግ ያለና ዕድሜዉ በሰላሳዎቹ አጋማሽ ላይ የሚገኝ አፍላ ጎልማሳ ነዉ:: የሰማያዊ ቀለም እጅጌ ጉርድ ሸሚዝ ለብሶ ጨፈቃ የሚያህል እጁ ሲታይ ጡንቻው ያስፈራራል። አልፎ አልፎ ከመኪና ላይ ሰራተኞች ጋር እየተላፋ በዚያ ክንዱ ጥምዝዝ እድርጎ ሲያስጮሀቸው እያየች ሸዋዬ በልሁ ተገኔ ትዝ ይላታል፤ ከመልካቸው በቀር የሰውነታቸው አቋም ተመሳሳይ ነውና።
ሰዓቱ ወደ አንድ ተኩል ሲጠጋ እንደ ምንም ጉዞ ተጀመረ። ያ ሠዓት ሔዋንና እናቷ ወደ አለታ ወንዶ መዳረሻቸወ ነው፡፡ ያ መንገድ ደግሞ የትራፊክ
ቁጥጥር ስለሌለበት በተለይ አነስተኛ ተሽከርካሪዎች ሰው በሰው ላይ እየጫኑ ሴንተርያ ተፈሪ ኬላ፣ ቀባዶ በተባሉና በሌሎችም ትንንሽ ከተሞች ሲደርሱ ተሳፋሪ
በማውጣት በማውረድ ጊዜ ያባከናሉ፡፡ አታካችና አሰልቺ መንገድ ነው፡፡ ሸዋዩ የተሳፈረችባት መኪናም ይህን ድርጊት ዘልላው አላለፈችም፡፡ ትቆም ትገተር ጀመር። ሽዋዬ በወጪ ወራጅ ጭቅጭቅ ጊዜው እያለፈባት ስትበሽቅ ስትናደድ ልቧ
ሊፈነዳ ደርሶ እያለለክች ልክ ከጠዋቱ አራት ሠዓት አካባቢ በአለታ ወንዶ መናኸሪያ ውስጥ ደረሰች፡፡ ወዲያው ዓይኗን በመናኸሪያው ዙሪያ ብታንከራትት
ሔዋንና እናቷ በአካባቢው የሉም። በእርግጥ ከአዲስ አበባ ወደ ክብረ መንግስት የሚሄደው አውቶብስ እዚያ መድረሻው ሰዓት ገና ነውና። በዚህ አጋጣሚ ሄዋንና
እናቷ ሻይ ቡና ለማለት ሄደው ሊሆን እንደሚችል ገምታ በመናኸሪያው አካባቢ የሚገኙትን ቡና ቤቶች በሙሉ ማሰስ ጀመረች፡፡ ነገር ግን እናቷና ሔዋን
አልታገኙም:: አሁንም እየተናደደች ፍለጋዋን ቀጠለች፡፡ ቢቸግራት እሷ በየቡና ቤቶች ስትሯሯጥ እናቷና ሔዋን በሌላ መንገድ ወደ መናኸሪያው ተመልሰው ይሆናል ብላ በማሱስ እንደገና ወደ መናኸሪያው ሮጠች:: ወደ ውስጥ ገብታ የመናህሪያውን ዙሪያ በዓይኗ ስትቃኝ በነበረችበት ወቅት ከበስተ ግራዋ በኩል የአንድ ወንድና ሴት ጭቅጭቅ ድንገት ከጆሮዋ ጥልቅ አለ፡
«አንቺ ባትዘገይብኝ ኖሮ እኮ እስካሁን ሄደን ነበር፡» በማለት ወንዱ በሴትዋ ላይ ይጮሃል።
ከአሁን በፊት ክብረ መንገስት የሚሄድ መኪና ይገኛል ብዬ እንዴት ልገምት?» አለች ሴትዮዋ::
«እንዴ! አለች ሸዋዬ እንደ መደንገጥ ብላ፡፡ ወደ ሰውየው ጠጋ በማለት «በቅርቡ ወደ ክብረ መንግስት የሄደ መኪና ነበር እንዴ?» ስትል ጠየቀችው።
«ሰው አጥቶ ሲጮህ ቆይቶ ከዲላ የመጣው አውቶብስ የሰው መአት
ሲዘረግፋለተ ግጥግጥ አድርጎ ጭኖ ሄደ፡፡» አላት ሰውየው እግረ መንገዱን ቁጭቱን ቀድሞ ለሚያነጋግራት ሴትዮ በመግለጽ ዓይነት፡፡
«ኣ» አለኝ ሸዋዬ ድንግጥ ብላ።
«ሙች ስልሽ!» ሰውየው አሁንም::
ሸዋዬ አንጀቷ ቁርጥ አለ። ከንፈሯን ንክስ አድርጋ በቁጭት ስሜት ራሷን ወዘወዘች በቃ! እናቷ ወይዘሮ ዘነቡና ታፈሡ የነገሯቸውን ሁሉ ተሸክመው ክብረ መንግስት ገብተዋል:: የብስጭቷ ብዛት ወገቧን አርገድግዶ ከአጥር ጥግ ድንጋይ ላይ አስቀመጣት። ራሷን በሁለት እጆቿ በመያዝ ወደ መሬት አቀረቀረች። ሀሳብ አወጣች አወረደች። ግን ምንም ማድረግ አልቻለችም፡፡
በዚያው ቦታ ላይ እንደተቀመጠች ሳታውቀው ሰዓቱ ሂዶ ኖሯል፡፡ ወደ
ስድስት ሰዓት አካባቢ ከአዲስ አበባ ወደ ክብረ መንግስት የሚሄደው አውቶብስ ደረሰና ጡሩንባውን እየነፋ ወደ መናኸሪያ'ው ገባ፡፡ እንደው ለምናልባቱ ብላ ወደ
መናኸሪያው በር ብትመለከትም ሔዋንና እናቷ ብቅ አላሉም፡፡ አውቶብሱ የሚያወርደውን አውርዶ የሚጭነውን ጭኖ ወደ ክበረ መንግስት ጉዞውን ቀጠሉ፡፡
የሸዋዬ ተስፋም ተሟጠጠ። ወደ ቤቷ በመመለስ በቀር ምርጫ አልነበራትም?
ወደ ዲላ ስለ መመለሷ ማሰብ ስትጀምር ቀደም ሲል ይታያት የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ትኩረት ወዳልሰጠችው ከቅጣጫ አተኮረች፡፡ ያቺ ከዲላ ይዛት
የመጣች ሊዮንችን እንደገና ወደ ዲላ ስትጭን ተመለከተች፡፡ ጠጋ ብላ ስትመለከት በመኪናዋ ውስጥ ሰው በሰው ላይ ተነባብሯል፡፡ የቆመው የተቀመጠው ተሳፋሪ አይተናነስም፡፡ ጨነቃት፡፡ ድንገት ወደ መናኸሪያው በር ዞር ብላ ስትመለከት ያን ወጠምሻ ሾፌር አየችው፡፡ አሁንም ቁልፎቹን እያቅጨለጨለ ከውጭ ወደ ውስጥ ይገባል። መኪናዋ አጠገብ እስከሚደርስ ጠበቀችና፡-
«የኔ ወንድም!» ስትል ጠራችው እንደ መሽኮርመም እያለች::
«አቤት!» እላት በጥቁር ፊቱ ላይ ወተት መስለው የሚታዩ ጥርሶቹን ፈገግ እያረገ፡፡
«መኪናህ በጣም ሞልቷል። እንዴት ይሻለኛል?» አለችው በመለማመጥ ዓይነት፡፡
«የመጣሽበት ጉዳይ አለቀ እንዴ?››
«ጨርሼ ነበር፡፡ መመለሻው ግን ጨነቀኝ::»
«እንደ ምንም ትሄጃለሻ!» አለና ሾፌሩ ወደ ረዳቱ ፊቱን መለስ አድርጎ
«እንዴት ነህ፣ ሞላ?» ሲል ረዳቱን ጠየቀው፡፡
«እየሞላ ነው::» አለው ረዳቱ የሚገባ ከተገኘ አሁንም ለመጫን የሚፈልግ መሆኑን በሚያመለክት አነጋገር፡፡
ሾፌሩ ሸዋዩንም ረዳቱንም ተውት አድርጎ ወደ ሌሉች ሰዎች ጠጋ ብሎ ያወራ ጀመር፡፡ ረዳቱ «ዲሳ ዲላ!» ማለቱን ቀጠለ፡፡ ሸዋዬ ግን ምናልባት ሾፌሩ ወንበር ፈልጎ ያስቀምጠኝ ይሆናል በማለት ቆማ ትጠባበቀው ጀመር። ከትንሽ
ቆይታ በኋላ ረዳቱ ሾፌሩን ተጣራ፡፡ ‹‹ማንዴ! ማንዴ! ግባና እንሂድ!» አለ፡፡
ሾፌሩ የረዳቱን ጥሪ በመቀበል ያወራቸው የነበሩትን ሰዎች ተሰናብቶ በመግቢያው በር በኩል ኸደ መኪናው ሲያመራ ሸዋዬ ከተል አለችና «ማንዴ እንዴት አረክልኝ ታድያ?» ስትል እንደ ማፈር እያለች ጠየቀችው ፡ የሾፌሩን ስም ከረዳቱ ጥሪ የወሰደችው ነው።
« አልገባሽም እንዴ?" አላት ሾፌሩ የራሱን መግቢያ በር ከፍቶ በእጁ ያዝ እያደረገ።
"መግቢያው ጨነቀኝ::»
ሾፌሩ ከመኪናወ ላይ ወጥቶ ከተቀመጠ በኋላ ወደ ኃላ ዞሮ ሲመስካት እውነትም መኪናው ሞልቶ ተጨናንቋል። መተንፈሻ የለም፡፡ ግን አንድ ነገር ትዝ አለው ሞተሩ ላይ ተቀምጠው ወደ ነበሩት ስዎች እየተመለከተ «እናንተ ተነሱ ሞተሩ ላይ መቀመጥ ክልከል ነው ወደ ኋላ! ወደ ኃላ ዳይ ዳይ» አላቸው፡፡
ሾፌሩ መሪ ይዞ የሚናገረው ሁሉ በተለይ በተቸገረ ተስፋሪ ዘንድ ተቀባይነት አለውና ሰዎቹ እያጉተመተሙ ቢሆን ተነሱ፡፡ ወዴኋላ እየተጋፋ ተሸጋሽገው
መቆማቸውን ከአረጋገጠ በኋላ ሾፈሩ ከመኪና ወርዶ ሸዋዬ
እንድትገባና ሞተር ላይ እንድትቀመጥ አደረጋት። ሸዋዬ ገባችና ፊቷን ወደ ሾፈሩ
አድርጋ እግሮቿን በማርሹ አጠገብ ኮርምታ በመቀመጥ ጉዞ ተጀመረ።
አስቸገርህ አይደል!» አለችው ሽዋዬ ሾፌሩ ማርሽ ሊቀይር ሲል እግሯ አወላክፎት የነበረ አጋጣሚን መነሻ በማድረግ።
«ምን ላድርግ፣ በሴት ልጅ አይጨክንም ብዬ ነዋ» አላት ሾፈሩ ቀና ብሎ በፈገግታ እያያት።
«ሁሉም እንዳተ በሆነ» አለች ሽዋዩ በመኪናው የፊት መስታወት ወዴፈት እያየችና ፈገግ እያለች፡፡ በዕለቱ ነጣ ያለ ሰማያዊ ኮትና ጉርድ ቀሚስ ለብሳለች:: ከጉልበቷ ጀምሮ እስክ ጡቷ ድረስ ሞላ ያለ ሰውነቷ በቀሚሷ ተወጥሮ ትርፁ
ይታያል። በዚያ ላይ አፍንጫ የሚሰነፍጥ ልዩ መዓዛ ያለው ሽቶ ተቀብታለች።
በመኪናዋ አካባቢ ይንጎራደድ ጀመር።
ሾፌሩ ጥቁርና ጠብሰቅ ያለ ሰውነት ያለው ነው: ቁመቱዎ ዘለግ ያለና ዕድሜዉ በሰላሳዎቹ አጋማሽ ላይ የሚገኝ አፍላ ጎልማሳ ነዉ:: የሰማያዊ ቀለም እጅጌ ጉርድ ሸሚዝ ለብሶ ጨፈቃ የሚያህል እጁ ሲታይ ጡንቻው ያስፈራራል። አልፎ አልፎ ከመኪና ላይ ሰራተኞች ጋር እየተላፋ በዚያ ክንዱ ጥምዝዝ እድርጎ ሲያስጮሀቸው እያየች ሸዋዬ በልሁ ተገኔ ትዝ ይላታል፤ ከመልካቸው በቀር የሰውነታቸው አቋም ተመሳሳይ ነውና።
ሰዓቱ ወደ አንድ ተኩል ሲጠጋ እንደ ምንም ጉዞ ተጀመረ። ያ ሠዓት ሔዋንና እናቷ ወደ አለታ ወንዶ መዳረሻቸወ ነው፡፡ ያ መንገድ ደግሞ የትራፊክ
ቁጥጥር ስለሌለበት በተለይ አነስተኛ ተሽከርካሪዎች ሰው በሰው ላይ እየጫኑ ሴንተርያ ተፈሪ ኬላ፣ ቀባዶ በተባሉና በሌሎችም ትንንሽ ከተሞች ሲደርሱ ተሳፋሪ
በማውጣት በማውረድ ጊዜ ያባከናሉ፡፡ አታካችና አሰልቺ መንገድ ነው፡፡ ሸዋዩ የተሳፈረችባት መኪናም ይህን ድርጊት ዘልላው አላለፈችም፡፡ ትቆም ትገተር ጀመር። ሽዋዬ በወጪ ወራጅ ጭቅጭቅ ጊዜው እያለፈባት ስትበሽቅ ስትናደድ ልቧ
ሊፈነዳ ደርሶ እያለለክች ልክ ከጠዋቱ አራት ሠዓት አካባቢ በአለታ ወንዶ መናኸሪያ ውስጥ ደረሰች፡፡ ወዲያው ዓይኗን በመናኸሪያው ዙሪያ ብታንከራትት
ሔዋንና እናቷ በአካባቢው የሉም። በእርግጥ ከአዲስ አበባ ወደ ክብረ መንግስት የሚሄደው አውቶብስ እዚያ መድረሻው ሰዓት ገና ነውና። በዚህ አጋጣሚ ሄዋንና
እናቷ ሻይ ቡና ለማለት ሄደው ሊሆን እንደሚችል ገምታ በመናኸሪያው አካባቢ የሚገኙትን ቡና ቤቶች በሙሉ ማሰስ ጀመረች፡፡ ነገር ግን እናቷና ሔዋን
አልታገኙም:: አሁንም እየተናደደች ፍለጋዋን ቀጠለች፡፡ ቢቸግራት እሷ በየቡና ቤቶች ስትሯሯጥ እናቷና ሔዋን በሌላ መንገድ ወደ መናኸሪያው ተመልሰው ይሆናል ብላ በማሱስ እንደገና ወደ መናኸሪያው ሮጠች:: ወደ ውስጥ ገብታ የመናህሪያውን ዙሪያ በዓይኗ ስትቃኝ በነበረችበት ወቅት ከበስተ ግራዋ በኩል የአንድ ወንድና ሴት ጭቅጭቅ ድንገት ከጆሮዋ ጥልቅ አለ፡
«አንቺ ባትዘገይብኝ ኖሮ እኮ እስካሁን ሄደን ነበር፡» በማለት ወንዱ በሴትዋ ላይ ይጮሃል።
ከአሁን በፊት ክብረ መንገስት የሚሄድ መኪና ይገኛል ብዬ እንዴት ልገምት?» አለች ሴትዮዋ::
«እንዴ! አለች ሸዋዬ እንደ መደንገጥ ብላ፡፡ ወደ ሰውየው ጠጋ በማለት «በቅርቡ ወደ ክብረ መንግስት የሄደ መኪና ነበር እንዴ?» ስትል ጠየቀችው።
«ሰው አጥቶ ሲጮህ ቆይቶ ከዲላ የመጣው አውቶብስ የሰው መአት
ሲዘረግፋለተ ግጥግጥ አድርጎ ጭኖ ሄደ፡፡» አላት ሰውየው እግረ መንገዱን ቁጭቱን ቀድሞ ለሚያነጋግራት ሴትዮ በመግለጽ ዓይነት፡፡
«ኣ» አለኝ ሸዋዬ ድንግጥ ብላ።
«ሙች ስልሽ!» ሰውየው አሁንም::
ሸዋዬ አንጀቷ ቁርጥ አለ። ከንፈሯን ንክስ አድርጋ በቁጭት ስሜት ራሷን ወዘወዘች በቃ! እናቷ ወይዘሮ ዘነቡና ታፈሡ የነገሯቸውን ሁሉ ተሸክመው ክብረ መንግስት ገብተዋል:: የብስጭቷ ብዛት ወገቧን አርገድግዶ ከአጥር ጥግ ድንጋይ ላይ አስቀመጣት። ራሷን በሁለት እጆቿ በመያዝ ወደ መሬት አቀረቀረች። ሀሳብ አወጣች አወረደች። ግን ምንም ማድረግ አልቻለችም፡፡
በዚያው ቦታ ላይ እንደተቀመጠች ሳታውቀው ሰዓቱ ሂዶ ኖሯል፡፡ ወደ
ስድስት ሰዓት አካባቢ ከአዲስ አበባ ወደ ክብረ መንግስት የሚሄደው አውቶብስ ደረሰና ጡሩንባውን እየነፋ ወደ መናኸሪያ'ው ገባ፡፡ እንደው ለምናልባቱ ብላ ወደ
መናኸሪያው በር ብትመለከትም ሔዋንና እናቷ ብቅ አላሉም፡፡ አውቶብሱ የሚያወርደውን አውርዶ የሚጭነውን ጭኖ ወደ ክበረ መንግስት ጉዞውን ቀጠሉ፡፡
የሸዋዬ ተስፋም ተሟጠጠ። ወደ ቤቷ በመመለስ በቀር ምርጫ አልነበራትም?
ወደ ዲላ ስለ መመለሷ ማሰብ ስትጀምር ቀደም ሲል ይታያት የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ትኩረት ወዳልሰጠችው ከቅጣጫ አተኮረች፡፡ ያቺ ከዲላ ይዛት
የመጣች ሊዮንችን እንደገና ወደ ዲላ ስትጭን ተመለከተች፡፡ ጠጋ ብላ ስትመለከት በመኪናዋ ውስጥ ሰው በሰው ላይ ተነባብሯል፡፡ የቆመው የተቀመጠው ተሳፋሪ አይተናነስም፡፡ ጨነቃት፡፡ ድንገት ወደ መናኸሪያው በር ዞር ብላ ስትመለከት ያን ወጠምሻ ሾፌር አየችው፡፡ አሁንም ቁልፎቹን እያቅጨለጨለ ከውጭ ወደ ውስጥ ይገባል። መኪናዋ አጠገብ እስከሚደርስ ጠበቀችና፡-
«የኔ ወንድም!» ስትል ጠራችው እንደ መሽኮርመም እያለች::
«አቤት!» እላት በጥቁር ፊቱ ላይ ወተት መስለው የሚታዩ ጥርሶቹን ፈገግ እያረገ፡፡
«መኪናህ በጣም ሞልቷል። እንዴት ይሻለኛል?» አለችው በመለማመጥ ዓይነት፡፡
«የመጣሽበት ጉዳይ አለቀ እንዴ?››
«ጨርሼ ነበር፡፡ መመለሻው ግን ጨነቀኝ::»
«እንደ ምንም ትሄጃለሻ!» አለና ሾፌሩ ወደ ረዳቱ ፊቱን መለስ አድርጎ
«እንዴት ነህ፣ ሞላ?» ሲል ረዳቱን ጠየቀው፡፡
«እየሞላ ነው::» አለው ረዳቱ የሚገባ ከተገኘ አሁንም ለመጫን የሚፈልግ መሆኑን በሚያመለክት አነጋገር፡፡
ሾፌሩ ሸዋዩንም ረዳቱንም ተውት አድርጎ ወደ ሌሉች ሰዎች ጠጋ ብሎ ያወራ ጀመር፡፡ ረዳቱ «ዲሳ ዲላ!» ማለቱን ቀጠለ፡፡ ሸዋዬ ግን ምናልባት ሾፌሩ ወንበር ፈልጎ ያስቀምጠኝ ይሆናል በማለት ቆማ ትጠባበቀው ጀመር። ከትንሽ
ቆይታ በኋላ ረዳቱ ሾፌሩን ተጣራ፡፡ ‹‹ማንዴ! ማንዴ! ግባና እንሂድ!» አለ፡፡
ሾፌሩ የረዳቱን ጥሪ በመቀበል ያወራቸው የነበሩትን ሰዎች ተሰናብቶ በመግቢያው በር በኩል ኸደ መኪናው ሲያመራ ሸዋዬ ከተል አለችና «ማንዴ እንዴት አረክልኝ ታድያ?» ስትል እንደ ማፈር እያለች ጠየቀችው ፡ የሾፌሩን ስም ከረዳቱ ጥሪ የወሰደችው ነው።
« አልገባሽም እንዴ?" አላት ሾፌሩ የራሱን መግቢያ በር ከፍቶ በእጁ ያዝ እያደረገ።
"መግቢያው ጨነቀኝ::»
ሾፌሩ ከመኪናወ ላይ ወጥቶ ከተቀመጠ በኋላ ወደ ኃላ ዞሮ ሲመስካት እውነትም መኪናው ሞልቶ ተጨናንቋል። መተንፈሻ የለም፡፡ ግን አንድ ነገር ትዝ አለው ሞተሩ ላይ ተቀምጠው ወደ ነበሩት ስዎች እየተመለከተ «እናንተ ተነሱ ሞተሩ ላይ መቀመጥ ክልከል ነው ወደ ኋላ! ወደ ኃላ ዳይ ዳይ» አላቸው፡፡
ሾፌሩ መሪ ይዞ የሚናገረው ሁሉ በተለይ በተቸገረ ተስፋሪ ዘንድ ተቀባይነት አለውና ሰዎቹ እያጉተመተሙ ቢሆን ተነሱ፡፡ ወዴኋላ እየተጋፋ ተሸጋሽገው
መቆማቸውን ከአረጋገጠ በኋላ ሾፈሩ ከመኪና ወርዶ ሸዋዬ
እንድትገባና ሞተር ላይ እንድትቀመጥ አደረጋት። ሸዋዬ ገባችና ፊቷን ወደ ሾፈሩ
አድርጋ እግሮቿን በማርሹ አጠገብ ኮርምታ በመቀመጥ ጉዞ ተጀመረ።
አስቸገርህ አይደል!» አለችው ሽዋዬ ሾፌሩ ማርሽ ሊቀይር ሲል እግሯ አወላክፎት የነበረ አጋጣሚን መነሻ በማድረግ።
«ምን ላድርግ፣ በሴት ልጅ አይጨክንም ብዬ ነዋ» አላት ሾፈሩ ቀና ብሎ በፈገግታ እያያት።
«ሁሉም እንዳተ በሆነ» አለች ሽዋዩ በመኪናው የፊት መስታወት ወዴፈት እያየችና ፈገግ እያለች፡፡ በዕለቱ ነጣ ያለ ሰማያዊ ኮትና ጉርድ ቀሚስ ለብሳለች:: ከጉልበቷ ጀምሮ እስክ ጡቷ ድረስ ሞላ ያለ ሰውነቷ በቀሚሷ ተወጥሮ ትርፁ
ይታያል። በዚያ ላይ አፍንጫ የሚሰነፍጥ ልዩ መዓዛ ያለው ሽቶ ተቀብታለች።
👍5
« እንዴት?» አላት ሾፌሩ ሳቅ ብሎ አየት እያደረጋት።
«ለሴትየዋ ልጅ ማዘንህ ነዋ!»
«ግን እኮ እናንተ ሴቶች ለወንድ ልጅ አታዝነም፡፡»
«የሚታዘንለትም አለ።»
«ምን አይነት ወንድ ሲሆን ነው የሚታዘንለት?» ሲል እየሳቀ ጠየቃት።
«ልክ እንደ አንተ ተባባሪ ሲሆን ነዋ!» አለችና ሽዋዬ ኪ.ኪ.ኪ. ኪ ብላ ሳቀች።
«ኦ ወደሽኛል!»
«መውደድ ሲሉህ ታዲያ..»
«በቃ ገብቶኛል፣ ውድድድ! አደረኩህ ማለት ነው በማለት ለራሱ ስቆ ሸዋዬንም አሳቃት።
«ተጫዋች ቢጤ ሳትሆን አትቀርም!»
«በተለይ አጫዋች ካገኘሁ ማ»
«እ!»
«ማጫወትም እችልበታለሁ፡፡»
ሁለቱም ሳቁ። ፈገግታቸው ከፊታቸው ላይ ሳይጠፋ ለአፍታ ያህል ዝም ዝም ካሉ በኋላ ሾፌሩ ቀጠለ፡፡ «ለምን መጥተሽ ነው?» ሲል ጠየቃት፡፡
«ሰዎች ፈልጌ ነበር፡፡ ግን እጥቻቸው ተመለስኩ፡፡ ሥራዬን ትቼ በከንቱ ለፋሁ።» አለችና ያ ቁጭቷ እንደገና ትዝ ብሏት ሳታውቀው ከንፈሯን ነከሰች፡፡
«የት ነው የምትሰሪው»
«መምህር ነኝ፡፡»
«ኦ! ምሁር ነሻ!»
«መባሌ ይሆን?ኪ ኪ ኪ ኪ!»
«ከአስተማሪ በሳይ ምሁር አለ እንዴ» አለና «እኛ ባለመማራችን አይደል የሰው መኪና ስንገፋ የምንኖረው አላት።
«ታዲያ የምትወፍሩት እናንተ» አለችው ሸዋዬ ያን መሪ የያዘ ጠብደል እጁን እየተመለከተች፡፡
«ሰርቀን ስለምንበላ እኮ ነው፡፡ አየሽ! እንዲህ እንደ አሁኑ ትርፍ ዕው ስንጭን ቦጨቅ የምናደርጋትን ገንዘብ አንሳሳላትም፤ ወዲያው ጉርስ ነው።አለበለዚያማ ይነቃብን ይመስለናል።»
«ለሚስቶቻችሁ ብትሰጧቸው እኮ…" ብላ ሳትጨርስ ሾፌሩ ቀደማት።
«ልብ ያላት ሴት የለችማ!»
«ባለቤትህ ገንዘብ መያዝ አትችልም'ን
«እሷማ ገንዘቡን ብቻ ሳይሆን እሷም አብራ ጠፋች፡፡»
«ማለት»
«ነገሩ ብዘ ነው የኔ እህት! አሁን አወርቼ አልጨርሰውም፡» አላትና
ሾፌሩ ለአፍታ ያህል ወደ ትካዜ ውስጥ ገባ። ሾፌሩ ባለ ትዳርና የአንድ ልጅ አባት ነበር፡፡ በስራው ፀባይ ከቦታ ወደ ቦታ አዘውትሮ ሲዘዋዋር በመሀል ሚስቱ ከሌላ
ወንድ ጋር ስትማግጥ ቆይታ የኋላ ኋሳ እንዲያውም ጭራሽ ከድታው ተሰውራዐትታያለች:: ውላ ኣድራ ያንኑ ያማገጣትን ሰውዬ አግብታ ትኖራለች፡፡ ሾፌሩ ከዚያ ወዲህ በወንደላጤነት ብቻውን ይኖራል:: ይህን ታሪክ ለሽዋዬ ነገራትና
«አያሳዝንም?» ሲል ጠየቃት።
«በእውነት በጣም ያሳዝናል!»
«ይኸውልሽ ያልተማረ ሰው ትርፉ ይኸ ብቻ ነው::»
«መማር ብቻ አይምሰልህ፤ ልብም ይጠይቃል::»
«ጎሽ!» በማለት ሾፌሩ ሸዋዬን አደነቀና «አየሽ፤ ይህን እንኳ ማለትሽ የመማርሽ ውጤት ነው::» አላት ፈገግ ብሎ አየት እያረጋት::
«ሀሳቤን ወደድከው?»
«በእውነት አሁንስ አንቺንም ወደድኩሽ»
«ተቀደድና!»
«ነገሩ ሞቶ»
በራሳቸው ወሬና ንግግር ሁለቱም ተሳሳቁና ለአፍታ ያህል በዝምታ ተጓዙ::ቆየት ብሎ ግን ሾፌሩ ወሬውን ቀጠለ።
«የኔስ ታሪክ ተዘከዘከ ያንቺስ?» ሲል ጠየቃት ሽዋዬን በማሽኮርመም ዓይነት ፈገግ ብሎ በቅንድቡ ሥር አየት እያረጋት፡፡
«ምን ይመስልሃል?» አለችው በመሽኮርመም ዓይነት አየት እያደረገችው::
«ልጆች ያሉሽ ይመስለኛል።»
ሽዋዬ አንገቷን በመነቅነቅ፡ «የለኝም የሚል መልስ ስጠችው::
«እንዴ! እስከ አሁን ምን ትጠብቂያለሽ?»
«ባል » አለችና ሽዋዬ ኪ ኪ ኪ ኪ ብላ ለራሷ ሳቀች።
«እስካአሁን አላገባሽም?
”ዘገየሁ? ኪ ኪ ኪ ኪ ኪ»
«ለነገሩ ይደርሳል፡፡» አለና «ምናልባት ዛሬ አብሮ ያዋለን ጌታ አብሮ ሊያሳድረን ይሆን እንዴ?» ብሎ ፈገግ እያለ ፊትለፊት ያያት ጀመር።
«ጭራሽ! ኪ ኪ ኪ ኪ ኪ»
«ማን ያውቃል ቢያጋባንስ»
«ሾፌርና አስተማሪ ተጋቡ ብሎ የዓለም ጋዜጠኛ ሁሉ ይስብሰባ ካ ካ ካ ካ ካ»
ሾፌሩና ሸዋዬ እንዲህና እንዲያ እየተባባሉ ሲጫወቱ ሳያውቁት ዲላ መዳረሻ ከሆነችው አጎራባች ላይ ደረሱ መኪናዋ በመንገድ ላይ ባሉ የተለያዩ ትንንሽ ከተሞች እየቆመች ተሳፋሪ ስትጭን ስታወርድ ቆይታለች። ሾፌሩ ግን
ቁም ሲሉት መቆምን ሂድ የባሰ መሄድ እንጂ ስአት እንደወረደ ስንት እንደተሳፈረ አያስታውስም፡፡ ቀልቡ ሁሉ ሸዋዩና ከጫዋታቸው ጋር ብቻ ነበር።
«እንዴ !ዲላ ደረስን እኮ አንቺ» አላት ዲሳ ከተማን ቁልቁል እየተመለከተ።
«አልታወቀህም አይደል?
«ኧረ ስም ሳንለዋወጥ እንዳንለያይ!» አለና ዞር ብሎ በፈገግታ እያያት እኔ ማንደፍሮ ጌጠነህ እባላለሁ፡፡ ሲያቆላምጠኝ ደግሞ ማንዴ! ግንድዬ ማንድያዬ
አለና «አንቺስ?» ሲል ጠየቃት።
«ስምህ አልበዛም? ኪ ኪ ኪ…»
«ማን ያውቃል ገና አንቺ ትጨምሪልኝ ይሆናል።»
«በዚሁ ላይ!»
«በይ ንገሪኛ!»
ሽዋዬ ትንሽ ስትሽኮረመሃ' ቆየችና ስሟን በአንድ ጥቅል እድርጋ ሳይሆን እየቆራረጠችና እንደ ዜማ መነሻ የመኪናውን ስፖንዳ በእግሯ እየመታች፡-
«መምህርት-ሽዋዬ-ተስፋዬ-- እባላለሁ» አለችው::
«እኔ ደሞ የሽዋ እልሻለሁ፡፡»
እንዴ አለች ሽዋዬ በሆዷ፡ ባርናባስ ወየሶም ለመጀመሪያ ጊዜ
ሲተዋወቃት በዚሁ ሁኔታና ስም አወጣጥ ነበር፡፡ በሆዷ ባርኔ፤ ማንዴን ተክተክ ልትሄድ ይሆን እንዴ? አለች፡፡ ትናንት የሽኝቱን ድግስ በልታለችና ከእንግዲህ
ባርባናስ ላልተወሰነ ጊዜ ትዝታ ሆኖ እንደሚቀር ታውቃለችና።
«ይመችሻል?» ሲል ማንደፍሮ ስለ ስም ቁልምጫ ጠየቃት፡፡
«ድሮም እጠራበት የነበረ ነው፡፡» አለችው ሳቅ እያለች፡፡
«እንግዲህ ተወርሳችኋል ብለሽ ንገሪያቸው፡፡» ብሎ ማንደፍሮ ለራሱ ስቆ መኪናዋ ከዲላ መናኸሪያ ወስጥ ገባች፡፡ በየመንገዱ ታጭቆ የነበረ ተሳፋሪ
ሁሉ መውረድ ጀመረ። ሽዋዬ ሞተር ላይ ስለነበረች መተላለፊያ ስላልነበራት መጠበቅ ነበረባትና ለአፍታ ያህል በዚያው በተቀመጠችበት ላይ ተቀምጣ ሳለች ማንደፍሮ አናገራት።
«በቃ መውረድሽ ነው?» አላት እጇን ያዝ አድርጎ።
«መኪናህ ታዲያ መኝታም አለው እንዴ? ኪ ኪ ኪ ኪ ኪ..»
«ባይኖረውም መኝታ ካለበት ቦታ ያደርሳል::»
«ኧረ ከዜ እንዳታሳድረኝ ፈራሁ
ልቀቀኝ! አለችው እየሳቀች።
«ቢያንስ አድራሻችን፡፡»
«ምን ያደርግልሀል?»
«አንቺን ፈልጌ አገኝበታለሁ፡፡
«ሌላ ጊዜ፡፡»
«ሌላው ጊዜ ሌላ ይሰራበታል፡፡ እድራሻ ግን ዛሬ ማለቅ አለበት:: አላትና ማንደፍሮ ይጠበቅባቸዋል ሲያደርጋት ሸዋዬ ተረታች።
«እሺ ስልኬን ያዘው» ማንደፍሮ
ደስ እያለው ወረቀትና እስክርብቶ ከኪሱ እያወጣ የቤት ነው
የስራ ቦታ ሲል ጠየቃት።
«የመስሪያ ቤት፡፡»
ማንደፍሮ ሽዋዬን ከመኪና አውርዶ ከሸኛት በኋላ ወዲያው ወደ ስልክ መደውያዉ ቦታ አመራ፡ ገና ሸዋዬ ከዓይኑ ሳትጠፋ በሰችው ስልክ ደውሎ
«መምህርት ሸዋዬን ፈልጌ ነበር» ብሎ ሲጠይቅ ዛሬ ስራ አልገባችም» የሚል ምላሽ ተሰጠው። የሸዋዩን አድራሻ በትክክል ማግኘቱን አረጋገጠ። ብዙ አልቆየም በዚያው ሰሞን ሸዋዬን በስልክ አግኝቶ ቀጠሮ አሲያዛት፡፡ በቀጠሮ ሠዓትና ቦታ
ተገናኙ።በሉ ጠጡ ተጫወቱ:: ማንደፍሮ የማሳረጊያ ጥያቄ ሲያቀርብ በሸዋዬ ተቃውሞ ለሌላ ቀን ተላለፈበት፡፡ ያም ቀን ደረሰ፡፡ ደግመው ተገናኙ፡፡ ሸዋዬ
ማንደፍሮን በቤቷ አስተናገደችው ደገሙ። ደጋገሙ። ሽዋዬ ማንደፍሮን ውድድ ማደፍሮም
በዚያው ልምድ!! ቋሚ መኖሪያው አዋሳ ቢሆንም ወደ ዲላ ብቅ ባለ
ቁጥር እድራሻው የሸዋዬ ቤት ሆነ፡፡ ዉል ያልያዘው ባልና ሚስትነት ተጀመረ፡፡ እነሆ ከዓመት በላይ ሆኗቸዋል፡፡....
💫ይቀጥላል💫
«ለሴትየዋ ልጅ ማዘንህ ነዋ!»
«ግን እኮ እናንተ ሴቶች ለወንድ ልጅ አታዝነም፡፡»
«የሚታዘንለትም አለ።»
«ምን አይነት ወንድ ሲሆን ነው የሚታዘንለት?» ሲል እየሳቀ ጠየቃት።
«ልክ እንደ አንተ ተባባሪ ሲሆን ነዋ!» አለችና ሽዋዬ ኪ.ኪ.ኪ. ኪ ብላ ሳቀች።
«ኦ ወደሽኛል!»
«መውደድ ሲሉህ ታዲያ..»
«በቃ ገብቶኛል፣ ውድድድ! አደረኩህ ማለት ነው በማለት ለራሱ ስቆ ሸዋዬንም አሳቃት።
«ተጫዋች ቢጤ ሳትሆን አትቀርም!»
«በተለይ አጫዋች ካገኘሁ ማ»
«እ!»
«ማጫወትም እችልበታለሁ፡፡»
ሁለቱም ሳቁ። ፈገግታቸው ከፊታቸው ላይ ሳይጠፋ ለአፍታ ያህል ዝም ዝም ካሉ በኋላ ሾፌሩ ቀጠለ፡፡ «ለምን መጥተሽ ነው?» ሲል ጠየቃት፡፡
«ሰዎች ፈልጌ ነበር፡፡ ግን እጥቻቸው ተመለስኩ፡፡ ሥራዬን ትቼ በከንቱ ለፋሁ።» አለችና ያ ቁጭቷ እንደገና ትዝ ብሏት ሳታውቀው ከንፈሯን ነከሰች፡፡
«የት ነው የምትሰሪው»
«መምህር ነኝ፡፡»
«ኦ! ምሁር ነሻ!»
«መባሌ ይሆን?ኪ ኪ ኪ ኪ!»
«ከአስተማሪ በሳይ ምሁር አለ እንዴ» አለና «እኛ ባለመማራችን አይደል የሰው መኪና ስንገፋ የምንኖረው አላት።
«ታዲያ የምትወፍሩት እናንተ» አለችው ሸዋዬ ያን መሪ የያዘ ጠብደል እጁን እየተመለከተች፡፡
«ሰርቀን ስለምንበላ እኮ ነው፡፡ አየሽ! እንዲህ እንደ አሁኑ ትርፍ ዕው ስንጭን ቦጨቅ የምናደርጋትን ገንዘብ አንሳሳላትም፤ ወዲያው ጉርስ ነው።አለበለዚያማ ይነቃብን ይመስለናል።»
«ለሚስቶቻችሁ ብትሰጧቸው እኮ…" ብላ ሳትጨርስ ሾፌሩ ቀደማት።
«ልብ ያላት ሴት የለችማ!»
«ባለቤትህ ገንዘብ መያዝ አትችልም'ን
«እሷማ ገንዘቡን ብቻ ሳይሆን እሷም አብራ ጠፋች፡፡»
«ማለት»
«ነገሩ ብዘ ነው የኔ እህት! አሁን አወርቼ አልጨርሰውም፡» አላትና
ሾፌሩ ለአፍታ ያህል ወደ ትካዜ ውስጥ ገባ። ሾፌሩ ባለ ትዳርና የአንድ ልጅ አባት ነበር፡፡ በስራው ፀባይ ከቦታ ወደ ቦታ አዘውትሮ ሲዘዋዋር በመሀል ሚስቱ ከሌላ
ወንድ ጋር ስትማግጥ ቆይታ የኋላ ኋሳ እንዲያውም ጭራሽ ከድታው ተሰውራዐትታያለች:: ውላ ኣድራ ያንኑ ያማገጣትን ሰውዬ አግብታ ትኖራለች፡፡ ሾፌሩ ከዚያ ወዲህ በወንደላጤነት ብቻውን ይኖራል:: ይህን ታሪክ ለሽዋዬ ነገራትና
«አያሳዝንም?» ሲል ጠየቃት።
«በእውነት በጣም ያሳዝናል!»
«ይኸውልሽ ያልተማረ ሰው ትርፉ ይኸ ብቻ ነው::»
«መማር ብቻ አይምሰልህ፤ ልብም ይጠይቃል::»
«ጎሽ!» በማለት ሾፌሩ ሸዋዬን አደነቀና «አየሽ፤ ይህን እንኳ ማለትሽ የመማርሽ ውጤት ነው::» አላት ፈገግ ብሎ አየት እያረጋት::
«ሀሳቤን ወደድከው?»
«በእውነት አሁንስ አንቺንም ወደድኩሽ»
«ተቀደድና!»
«ነገሩ ሞቶ»
በራሳቸው ወሬና ንግግር ሁለቱም ተሳሳቁና ለአፍታ ያህል በዝምታ ተጓዙ::ቆየት ብሎ ግን ሾፌሩ ወሬውን ቀጠለ።
«የኔስ ታሪክ ተዘከዘከ ያንቺስ?» ሲል ጠየቃት ሽዋዬን በማሽኮርመም ዓይነት ፈገግ ብሎ በቅንድቡ ሥር አየት እያረጋት፡፡
«ምን ይመስልሃል?» አለችው በመሽኮርመም ዓይነት አየት እያደረገችው::
«ልጆች ያሉሽ ይመስለኛል።»
ሽዋዬ አንገቷን በመነቅነቅ፡ «የለኝም የሚል መልስ ስጠችው::
«እንዴ! እስከ አሁን ምን ትጠብቂያለሽ?»
«ባል » አለችና ሽዋዬ ኪ ኪ ኪ ኪ ብላ ለራሷ ሳቀች።
«እስካአሁን አላገባሽም?
”ዘገየሁ? ኪ ኪ ኪ ኪ ኪ»
«ለነገሩ ይደርሳል፡፡» አለና «ምናልባት ዛሬ አብሮ ያዋለን ጌታ አብሮ ሊያሳድረን ይሆን እንዴ?» ብሎ ፈገግ እያለ ፊትለፊት ያያት ጀመር።
«ጭራሽ! ኪ ኪ ኪ ኪ ኪ»
«ማን ያውቃል ቢያጋባንስ»
«ሾፌርና አስተማሪ ተጋቡ ብሎ የዓለም ጋዜጠኛ ሁሉ ይስብሰባ ካ ካ ካ ካ ካ»
ሾፌሩና ሸዋዬ እንዲህና እንዲያ እየተባባሉ ሲጫወቱ ሳያውቁት ዲላ መዳረሻ ከሆነችው አጎራባች ላይ ደረሱ መኪናዋ በመንገድ ላይ ባሉ የተለያዩ ትንንሽ ከተሞች እየቆመች ተሳፋሪ ስትጭን ስታወርድ ቆይታለች። ሾፌሩ ግን
ቁም ሲሉት መቆምን ሂድ የባሰ መሄድ እንጂ ስአት እንደወረደ ስንት እንደተሳፈረ አያስታውስም፡፡ ቀልቡ ሁሉ ሸዋዩና ከጫዋታቸው ጋር ብቻ ነበር።
«እንዴ !ዲላ ደረስን እኮ አንቺ» አላት ዲሳ ከተማን ቁልቁል እየተመለከተ።
«አልታወቀህም አይደል?
«ኧረ ስም ሳንለዋወጥ እንዳንለያይ!» አለና ዞር ብሎ በፈገግታ እያያት እኔ ማንደፍሮ ጌጠነህ እባላለሁ፡፡ ሲያቆላምጠኝ ደግሞ ማንዴ! ግንድዬ ማንድያዬ
አለና «አንቺስ?» ሲል ጠየቃት።
«ስምህ አልበዛም? ኪ ኪ ኪ…»
«ማን ያውቃል ገና አንቺ ትጨምሪልኝ ይሆናል።»
«በዚሁ ላይ!»
«በይ ንገሪኛ!»
ሽዋዬ ትንሽ ስትሽኮረመሃ' ቆየችና ስሟን በአንድ ጥቅል እድርጋ ሳይሆን እየቆራረጠችና እንደ ዜማ መነሻ የመኪናውን ስፖንዳ በእግሯ እየመታች፡-
«መምህርት-ሽዋዬ-ተስፋዬ-- እባላለሁ» አለችው::
«እኔ ደሞ የሽዋ እልሻለሁ፡፡»
እንዴ አለች ሽዋዬ በሆዷ፡ ባርናባስ ወየሶም ለመጀመሪያ ጊዜ
ሲተዋወቃት በዚሁ ሁኔታና ስም አወጣጥ ነበር፡፡ በሆዷ ባርኔ፤ ማንዴን ተክተክ ልትሄድ ይሆን እንዴ? አለች፡፡ ትናንት የሽኝቱን ድግስ በልታለችና ከእንግዲህ
ባርባናስ ላልተወሰነ ጊዜ ትዝታ ሆኖ እንደሚቀር ታውቃለችና።
«ይመችሻል?» ሲል ማንደፍሮ ስለ ስም ቁልምጫ ጠየቃት፡፡
«ድሮም እጠራበት የነበረ ነው፡፡» አለችው ሳቅ እያለች፡፡
«እንግዲህ ተወርሳችኋል ብለሽ ንገሪያቸው፡፡» ብሎ ማንደፍሮ ለራሱ ስቆ መኪናዋ ከዲላ መናኸሪያ ወስጥ ገባች፡፡ በየመንገዱ ታጭቆ የነበረ ተሳፋሪ
ሁሉ መውረድ ጀመረ። ሽዋዬ ሞተር ላይ ስለነበረች መተላለፊያ ስላልነበራት መጠበቅ ነበረባትና ለአፍታ ያህል በዚያው በተቀመጠችበት ላይ ተቀምጣ ሳለች ማንደፍሮ አናገራት።
«በቃ መውረድሽ ነው?» አላት እጇን ያዝ አድርጎ።
«መኪናህ ታዲያ መኝታም አለው እንዴ? ኪ ኪ ኪ ኪ ኪ..»
«ባይኖረውም መኝታ ካለበት ቦታ ያደርሳል::»
«ኧረ ከዜ እንዳታሳድረኝ ፈራሁ
ልቀቀኝ! አለችው እየሳቀች።
«ቢያንስ አድራሻችን፡፡»
«ምን ያደርግልሀል?»
«አንቺን ፈልጌ አገኝበታለሁ፡፡
«ሌላ ጊዜ፡፡»
«ሌላው ጊዜ ሌላ ይሰራበታል፡፡ እድራሻ ግን ዛሬ ማለቅ አለበት:: አላትና ማንደፍሮ ይጠበቅባቸዋል ሲያደርጋት ሸዋዬ ተረታች።
«እሺ ስልኬን ያዘው» ማንደፍሮ
ደስ እያለው ወረቀትና እስክርብቶ ከኪሱ እያወጣ የቤት ነው
የስራ ቦታ ሲል ጠየቃት።
«የመስሪያ ቤት፡፡»
ማንደፍሮ ሽዋዬን ከመኪና አውርዶ ከሸኛት በኋላ ወዲያው ወደ ስልክ መደውያዉ ቦታ አመራ፡ ገና ሸዋዬ ከዓይኑ ሳትጠፋ በሰችው ስልክ ደውሎ
«መምህርት ሸዋዬን ፈልጌ ነበር» ብሎ ሲጠይቅ ዛሬ ስራ አልገባችም» የሚል ምላሽ ተሰጠው። የሸዋዩን አድራሻ በትክክል ማግኘቱን አረጋገጠ። ብዙ አልቆየም በዚያው ሰሞን ሸዋዬን በስልክ አግኝቶ ቀጠሮ አሲያዛት፡፡ በቀጠሮ ሠዓትና ቦታ
ተገናኙ።በሉ ጠጡ ተጫወቱ:: ማንደፍሮ የማሳረጊያ ጥያቄ ሲያቀርብ በሸዋዬ ተቃውሞ ለሌላ ቀን ተላለፈበት፡፡ ያም ቀን ደረሰ፡፡ ደግመው ተገናኙ፡፡ ሸዋዬ
ማንደፍሮን በቤቷ አስተናገደችው ደገሙ። ደጋገሙ። ሽዋዬ ማንደፍሮን ውድድ ማደፍሮም
በዚያው ልምድ!! ቋሚ መኖሪያው አዋሳ ቢሆንም ወደ ዲላ ብቅ ባለ
ቁጥር እድራሻው የሸዋዬ ቤት ሆነ፡፡ ዉል ያልያዘው ባልና ሚስትነት ተጀመረ፡፡ እነሆ ከዓመት በላይ ሆኗቸዋል፡፡....
💫ይቀጥላል💫
👍15
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...“ቁስቋም ብዙ ነገር ሰጥታኛለች፣ ወንድ ልዥ ደሞ ብትሰጠኝ።”
“ትሰጥሻለች። ምን ይሳናታል? አሁን ስለሱ አታስቢ።”
ሆዷ እየገፋ ሲመጣ፣ ጭንቀቷ በረታ። ሴት በመውለዷ ባትከፋም፣ ወንድ አለመውለዷ ቤተመንግሥት ውስጥ ሊኖረኝ ይችላል ብላ ያሰበችውን ቦታ የሚያሳጣት መሰላት።
ይበልጡንም ደግሞ ወህኒ
አምባ ያሉ የነገሥታት ዘሮች የሚወለደው ወንድ ቢሆን ሐዘናቸውን፣ ሴት ብትሆን ደግሞ ደስታቸውንና የበካፋን ተስፋ መጨናገፍ እያሰበች መንፈሷ ተበጠበጠ። የጐንደርን ታቦታት ሁሉ ተማጸነች። የእሷ
ቋረኝነት ያብከነከናቸው መሣፍንትና መኳንንት ደግሞ በካፋ ሲሄዱ ቋረኛ አልጋው ላይ የመውጣቱ ጉዳይ ሲያሳስባቸው፣ ሲያነጋግራቸውና ልባቸውን ሲሰቅለው እሷ የበለጠ ጭንቀት ውስጥ ገባች።
የቤተመንግሥት ባለሟሉ፣ የበካፋ ደጋፊ መኳንንትና ሕዝቡ ግን
በእነሱ ዘንድ ተወዳጅነትን እያተረፈች ለመጣችው፣ ለእሷ... ለምንትዋብ ወንድ ልጅ እንድትወልድ ተመኙላት።
ለወራት ቤተመንግሥት ግቢ ውስጥ፣ በየቤቱና በየመንደሩ ወሬው ተጋጋለ፤ ሞኝ መቆሚያ ላይ ተሟሟቀ፤ ጃን ተከል ላይ ተፋፋመ።የጃን ተከል ደንበኞች ወደ ሞኝ መቆሚያ ተጨማሪ ወሬ ለማሳደድ አሽቆለቆሉ። የሞኝ መቆሚያዎቹ ወደ ጃን ተከል በጥድፊያ አሻቀቡ።
መጽሐፍ ገላጩና ኮከብ ቆጣሪው ገሚሱ ወንድ፣ ሌላው ሴት ነው
ሲል ተነበየ። ገበሬው በየእርሻው፣ ነጋዴው በገበያው ላይ፣ ሴቶች ወንዝ ዳር፣ ሽማግሌና ወጣት በየጎጡ እሰጥ አገባ ያዙ፤ ተወራረዱ። የንግርት
ዓይነቶች ተወሱ። የቆራጣ ገዳም እመምኔቷ፣ የወለተጴጥሮስ ትንቢት ተወራ፣ የሰማው ላልሰማው አስተላለፈ። ወሬው ጐንደርን ተሻግሮ በየግዛቱ ተናፈሰ። ቀድሞ ስለነገሥታት የተነገሩ ሌሎች ንግርቶች
ሁሉ ለማመሳከሪያነት ቀረቡ፣ ተመረመሩ፣ ተተነተኑ።
ሃገር በወሬ ታመሰች። ወንድ ነው ሲሏት ጮቤ ስትረግጥ፣ ሴት ናት
ሲሏት ስትተክዝ ከረመች።
ምንትዋብ በበኩሏ ቀናቱ ሲያዘግሙባት፣ ወራቱ እንደ ገመድ ሲጎተቱባት ቆይታ አንድ ሌሊት ምጥ ያዛት። እናቷና አያቷ የነገሥታቱ አዋላጅ የሆኑትን ሴት በፍጥነት አስመጡ። ምንትዋብ ሌሊቱን በሙሉ ስታምጥ፣ ሴቱ “ማርያም”፣ “ማርያም” ሲል፣ በካፋ በጭንቀት ቁጭ
ብድግ ሲሉ፣ ሲጸልዩ፣ ካህናት ምህላ ሲያወርዱና የቤተመንግሥት ባለሟሎች ሲንቆራጠጡ ቆይተው ንጋት ላይ የመጀመሪያው ዕልልታ ተሰማ። በሰላም የመገላገሏ ዜና በመኾኑ ለአፄው የአፍታ እፎይታ
ቢሰጣቸውም የሕጻኑን ጸታ ለመለየት ዕልልታውን መቁጠር ጀመሩ።
ዕልልታው ተደገመ፤ የበካፋ ጭንቀትም ናረ፤ ሦስተኛውና የመጨረሻው ዕልልታ ይሰማና ወሽመጤን ይቆርጠው ይኾን ወይስ ይቀጥላል? የሚለው ጭንቀት በእያንዳንዱ ዕልልታ መሃል ያለችዋን ቅጽበት ዝንተዓለም እስክትመስል ድረስ ለጠጣት። ሦስተኛው ዕልልታ
ተሰማ። እዚኸ ላይ የበካፋ የልብ ትርታ ፀጥ አለ፤ ሌላ ዕልልታ ካልተሰማ አልቦ አልጋ ወራሽ የሚለው ሥጋት ሰቅዞ ይዟቸዋል። የጠላቶቻቸውን መደሰት፣ የወዳጆቻቸውን መሳቀቅ እየቃኙ ሳለ፣ አራተኛው የዕልልታ
ድምጽ መጣ። ወንድ ልጅ! አምስተኛውን፣ ስድስተኛውንና ሰባተኛውን ዕልልታ መስማት አላስፈለጋቸውም፤ ወንድ ልጅ ተወልዶላቸዋል! ዜናውን በመላ ቤተመንግሥቱ ግቢ ውስጥ ሲያስተጋቡት፣ ግቢው
ትርምስምሱ ወጣ።
ምንትዋብ ድካም ላይ ብትሆንም ደስታዋ ወሰን አጣ፣ በጭንቀት
የተኮማተረው ግንባሯ ተፍታታ፤ ቁስቋም ማርያምን አመሰገነች።
አፄ በካፋ በጭንቀት የሙጥኝ ይዘውት የነበረውን የጸሎት
መጽሐፋቸውን አስቀምጠው ከመኝታ ክፍላቸው ወጡ።
ምንትዋብ ወዳለችበት ገሰገሱ። ምንትዋብ እስክትጸዳዳ ጠብቀው
ሲገቡ፣ እየደጋገሙ፣ “እንኳን ማርያም ማረችሽ” አሏት። እንኰዬ
ህጻኑን ኣቅፈው ሲያሳይዋቸው የደስታ እንባ ተናነቃቸው። አልጋ ወራሽ በማግኘታቸው ሩፋኤልንና ከአንገርብ ወንዝ በስቲያ ደፈጫ የተከሏትን ኪዳነ ምሕረትን አመሰገኑ፤ ውለታቸውን በወርቅ እንደሚከፍሉ ቃል ገቡ።
ቤተመንግሥቱ ውስጥ ታላቅ ፈንጠዝያ ሆነ። ወዲያው ስፍር ቁጥር የሌለው የግባት ነፍጥ ወደላይ ተተኮሰ። የአካባቢው ሰው “ወንድ ነው!
ወንድ ነው!” እያለ ጃን ተከል ግልብጥ ብሎ ወጣ። ሴቶች ዕልልታቸውን አቀለጡት። ጐንደር የምሥራቹ ደረሳት፤ ፈነደቀች። ራቅ ካሉ ቦታዎች ሳይቀር ጐንደሬዎች እየከነፉ ጃን ተከል ደረሱ።
እቴጌ ወንድ ልዥ ተገላገሉ! ሰባት ግዝየ ሲተኮስ ቆጥሬያለሁ።
ወንድ ነው። ንጉሡ አልጋ ወራሽ አገኙ!” ይላል አንዱ።
“ሦስት ቆጥሬ ሴት ትሆን? ስል ዐራት ሲደገም እንግዲያማ ሰባት
ነው ሚሆን። ወንድ ነው ብየ ስሮጥ መጣሁ” ይላል ሌላው።
የዕጣና የውርርድ አሸናፊዎች የድል ዋጋቸውን ጠየቁ።
ንግርቶች ሁሉ እንደገና ተነገሩ። የቅድስት ወለተጴጥርስ ትንቢት
ተነሣ። “የሷ ንግርት መሬት አይወድቅም” ተባለ። በየደብሩ ካህናት ደወል አሰሙ። ዘመሩ፣ አሸበሸቡ። መነኮሳት ሕልማቸውን ተለወዋጡ: ደስታ በደስታ ሆኑ።
የበካፋ የሥልጣን ተቀናቃኞች ወሬውን ሲሰሙ ደነገጡ፤ ተስፋቸው እንደ እንፋሎት ተነነ። የማስመሰል ካባ የደረቡ አንጀታቸው ያረረ፣ወንድ ልጅ በመወለዱ ከልብ የተደሰቱ መኳንንት፣ ካህናትና ሊቃውንት
ከቅርብና ከሩቅ ደስታቸውን ለመግለፅ ወደ ቤተመንግሥት ጎረፉ።
ለሕጻኑም መልካም ምኞታቸውን አዥጎደጎዱ። ሕጻኑ በአያቱ፣ በአፄ ኣድያም ሰገድ ኢያሱ ስም ተጠራ። ግብር በየቀኑ ገባ። ኢያሱ፣ በወጉ መሠረት በአርባ ቀኑ ክርስትና ተነሣ።
ኢያሱ ከተወለደ በኋላ፣ የመጀመሪያው መስቀል ነው። ለአፄ በካፋ ዓመታዊ ሠራዊት ግባት ከፍተኛ ዝግጅት እየተደረገ ነው። እንደ ጎጃምና ትግራይ ካሉ ራቅ ካሉ ግዛቶች የሚመጡ አስተዳዳሪ መኳንንት
ክረምቱ ሳይገባ ግንቦት ወር ላይ እያንዳንዳቸው ሠራዊታቸውን
ይዘው ጐንደር ሲገቡ፣ እንደ ስሜንና ቤገምድር ካሉ ቅርብ ቦታዎች የሚመጡት ደግሞ ዐዲስ ዓመትን ቤታቸው ውለው ሠራዊታቸውን ይዘው ጐንደር ገብተዋል። ቤተመንግሥት ዙርያ ለየግላቸውና ይዘውት
ለመጡት ሠራዊት ድንኳን ተተክሎላቸው እዚያው አርፈዋል።
ምንትዋብና አያቷ ስለ ሠራዊት ግባቱ አስፈላጊነት ሲነጋገሩ
አያትየው፣ ነገሥታቱ እኼን በዓል ሚያደርጉት አንድም እንግዲህ
ወታደራዊ ጉልበታቸውን ለማሳየት...” ብለው ሲጀምሩ አቋረጠቻቸው።
“ለማን ነው ሚያሳዩት?”
“ለሁሉም። እሱ ብቻ ማዶል። የመኳንንቱን ታማኝነት ለማረጋገጥም ሲሉ ነው። ሌላ ደሞ... ደንብ ሲያወጡ ወይም አዋጅ ሲነግሩ መኳንንቱ
በየግዛታቸው ያነን ደንብና አዋጅ በተመሳሳይ መንገድ እንዲያስከብሩ ጭምር ነው። ሌላው ደሞ መቸም ንጉሡ መኳንንቱ እንዳያምጹባቸው...
ተቀይመዋቸው ከሆነ ደሞ ለማረጋጋትና ሰላም ለመፍጠር በጋብቻ ሚተሳሰሩበትም ግዝየ ነው። በዝኸ ግዝየ አንድ የተቀየመ መኰንን አሞኛል ብሎ ሊቀር ይችላል። እናም እኼ ግዝየ ጃንሆይ አለ ነገር ሚሉበት፣ ብዙ ነገር ሚያውቁበትና ሚስተካከል ኻለም ተሎ ብለው ሚያስተካክሉበትም ግዝየ ነው” አሏት።
የበዓሉ ዕለት፣ ምንትዋብ ከአፄ በካፋ ጎን ድባብ ተይዞላት አደባባይ ወጣች። ሥርዐቱን ለማየት እጅግ ጓግታለች። ከንጉሠ ነገሥቱ ጎን ተቀመች። ጐንደሬዎችም ይህን ታላቅ በዓል ለመታደም ሥራቸውን
ነቅለው ወጥተዋል። ፎካሪዎች በየተራ እየወጡ ወደላይ ወደታች እያሉ ፎከሩ፣ ሽለሉ። ንጉሠ ነገሥቱን አወደሱ፤ አመሰገኑ።ሽለላውና ፉከራው ሲቆም፣ በአጋፋሪ መሪነት ታላቁ ስልፍ ተጀመረ።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
...“ቁስቋም ብዙ ነገር ሰጥታኛለች፣ ወንድ ልዥ ደሞ ብትሰጠኝ።”
“ትሰጥሻለች። ምን ይሳናታል? አሁን ስለሱ አታስቢ።”
ሆዷ እየገፋ ሲመጣ፣ ጭንቀቷ በረታ። ሴት በመውለዷ ባትከፋም፣ ወንድ አለመውለዷ ቤተመንግሥት ውስጥ ሊኖረኝ ይችላል ብላ ያሰበችውን ቦታ የሚያሳጣት መሰላት።
ይበልጡንም ደግሞ ወህኒ
አምባ ያሉ የነገሥታት ዘሮች የሚወለደው ወንድ ቢሆን ሐዘናቸውን፣ ሴት ብትሆን ደግሞ ደስታቸውንና የበካፋን ተስፋ መጨናገፍ እያሰበች መንፈሷ ተበጠበጠ። የጐንደርን ታቦታት ሁሉ ተማጸነች። የእሷ
ቋረኝነት ያብከነከናቸው መሣፍንትና መኳንንት ደግሞ በካፋ ሲሄዱ ቋረኛ አልጋው ላይ የመውጣቱ ጉዳይ ሲያሳስባቸው፣ ሲያነጋግራቸውና ልባቸውን ሲሰቅለው እሷ የበለጠ ጭንቀት ውስጥ ገባች።
የቤተመንግሥት ባለሟሉ፣ የበካፋ ደጋፊ መኳንንትና ሕዝቡ ግን
በእነሱ ዘንድ ተወዳጅነትን እያተረፈች ለመጣችው፣ ለእሷ... ለምንትዋብ ወንድ ልጅ እንድትወልድ ተመኙላት።
ለወራት ቤተመንግሥት ግቢ ውስጥ፣ በየቤቱና በየመንደሩ ወሬው ተጋጋለ፤ ሞኝ መቆሚያ ላይ ተሟሟቀ፤ ጃን ተከል ላይ ተፋፋመ።የጃን ተከል ደንበኞች ወደ ሞኝ መቆሚያ ተጨማሪ ወሬ ለማሳደድ አሽቆለቆሉ። የሞኝ መቆሚያዎቹ ወደ ጃን ተከል በጥድፊያ አሻቀቡ።
መጽሐፍ ገላጩና ኮከብ ቆጣሪው ገሚሱ ወንድ፣ ሌላው ሴት ነው
ሲል ተነበየ። ገበሬው በየእርሻው፣ ነጋዴው በገበያው ላይ፣ ሴቶች ወንዝ ዳር፣ ሽማግሌና ወጣት በየጎጡ እሰጥ አገባ ያዙ፤ ተወራረዱ። የንግርት
ዓይነቶች ተወሱ። የቆራጣ ገዳም እመምኔቷ፣ የወለተጴጥሮስ ትንቢት ተወራ፣ የሰማው ላልሰማው አስተላለፈ። ወሬው ጐንደርን ተሻግሮ በየግዛቱ ተናፈሰ። ቀድሞ ስለነገሥታት የተነገሩ ሌሎች ንግርቶች
ሁሉ ለማመሳከሪያነት ቀረቡ፣ ተመረመሩ፣ ተተነተኑ።
ሃገር በወሬ ታመሰች። ወንድ ነው ሲሏት ጮቤ ስትረግጥ፣ ሴት ናት
ሲሏት ስትተክዝ ከረመች።
ምንትዋብ በበኩሏ ቀናቱ ሲያዘግሙባት፣ ወራቱ እንደ ገመድ ሲጎተቱባት ቆይታ አንድ ሌሊት ምጥ ያዛት። እናቷና አያቷ የነገሥታቱ አዋላጅ የሆኑትን ሴት በፍጥነት አስመጡ። ምንትዋብ ሌሊቱን በሙሉ ስታምጥ፣ ሴቱ “ማርያም”፣ “ማርያም” ሲል፣ በካፋ በጭንቀት ቁጭ
ብድግ ሲሉ፣ ሲጸልዩ፣ ካህናት ምህላ ሲያወርዱና የቤተመንግሥት ባለሟሎች ሲንቆራጠጡ ቆይተው ንጋት ላይ የመጀመሪያው ዕልልታ ተሰማ። በሰላም የመገላገሏ ዜና በመኾኑ ለአፄው የአፍታ እፎይታ
ቢሰጣቸውም የሕጻኑን ጸታ ለመለየት ዕልልታውን መቁጠር ጀመሩ።
ዕልልታው ተደገመ፤ የበካፋ ጭንቀትም ናረ፤ ሦስተኛውና የመጨረሻው ዕልልታ ይሰማና ወሽመጤን ይቆርጠው ይኾን ወይስ ይቀጥላል? የሚለው ጭንቀት በእያንዳንዱ ዕልልታ መሃል ያለችዋን ቅጽበት ዝንተዓለም እስክትመስል ድረስ ለጠጣት። ሦስተኛው ዕልልታ
ተሰማ። እዚኸ ላይ የበካፋ የልብ ትርታ ፀጥ አለ፤ ሌላ ዕልልታ ካልተሰማ አልቦ አልጋ ወራሽ የሚለው ሥጋት ሰቅዞ ይዟቸዋል። የጠላቶቻቸውን መደሰት፣ የወዳጆቻቸውን መሳቀቅ እየቃኙ ሳለ፣ አራተኛው የዕልልታ
ድምጽ መጣ። ወንድ ልጅ! አምስተኛውን፣ ስድስተኛውንና ሰባተኛውን ዕልልታ መስማት አላስፈለጋቸውም፤ ወንድ ልጅ ተወልዶላቸዋል! ዜናውን በመላ ቤተመንግሥቱ ግቢ ውስጥ ሲያስተጋቡት፣ ግቢው
ትርምስምሱ ወጣ።
ምንትዋብ ድካም ላይ ብትሆንም ደስታዋ ወሰን አጣ፣ በጭንቀት
የተኮማተረው ግንባሯ ተፍታታ፤ ቁስቋም ማርያምን አመሰገነች።
አፄ በካፋ በጭንቀት የሙጥኝ ይዘውት የነበረውን የጸሎት
መጽሐፋቸውን አስቀምጠው ከመኝታ ክፍላቸው ወጡ።
ምንትዋብ ወዳለችበት ገሰገሱ። ምንትዋብ እስክትጸዳዳ ጠብቀው
ሲገቡ፣ እየደጋገሙ፣ “እንኳን ማርያም ማረችሽ” አሏት። እንኰዬ
ህጻኑን ኣቅፈው ሲያሳይዋቸው የደስታ እንባ ተናነቃቸው። አልጋ ወራሽ በማግኘታቸው ሩፋኤልንና ከአንገርብ ወንዝ በስቲያ ደፈጫ የተከሏትን ኪዳነ ምሕረትን አመሰገኑ፤ ውለታቸውን በወርቅ እንደሚከፍሉ ቃል ገቡ።
ቤተመንግሥቱ ውስጥ ታላቅ ፈንጠዝያ ሆነ። ወዲያው ስፍር ቁጥር የሌለው የግባት ነፍጥ ወደላይ ተተኮሰ። የአካባቢው ሰው “ወንድ ነው!
ወንድ ነው!” እያለ ጃን ተከል ግልብጥ ብሎ ወጣ። ሴቶች ዕልልታቸውን አቀለጡት። ጐንደር የምሥራቹ ደረሳት፤ ፈነደቀች። ራቅ ካሉ ቦታዎች ሳይቀር ጐንደሬዎች እየከነፉ ጃን ተከል ደረሱ።
እቴጌ ወንድ ልዥ ተገላገሉ! ሰባት ግዝየ ሲተኮስ ቆጥሬያለሁ።
ወንድ ነው። ንጉሡ አልጋ ወራሽ አገኙ!” ይላል አንዱ።
“ሦስት ቆጥሬ ሴት ትሆን? ስል ዐራት ሲደገም እንግዲያማ ሰባት
ነው ሚሆን። ወንድ ነው ብየ ስሮጥ መጣሁ” ይላል ሌላው።
የዕጣና የውርርድ አሸናፊዎች የድል ዋጋቸውን ጠየቁ።
ንግርቶች ሁሉ እንደገና ተነገሩ። የቅድስት ወለተጴጥርስ ትንቢት
ተነሣ። “የሷ ንግርት መሬት አይወድቅም” ተባለ። በየደብሩ ካህናት ደወል አሰሙ። ዘመሩ፣ አሸበሸቡ። መነኮሳት ሕልማቸውን ተለወዋጡ: ደስታ በደስታ ሆኑ።
የበካፋ የሥልጣን ተቀናቃኞች ወሬውን ሲሰሙ ደነገጡ፤ ተስፋቸው እንደ እንፋሎት ተነነ። የማስመሰል ካባ የደረቡ አንጀታቸው ያረረ፣ወንድ ልጅ በመወለዱ ከልብ የተደሰቱ መኳንንት፣ ካህናትና ሊቃውንት
ከቅርብና ከሩቅ ደስታቸውን ለመግለፅ ወደ ቤተመንግሥት ጎረፉ።
ለሕጻኑም መልካም ምኞታቸውን አዥጎደጎዱ። ሕጻኑ በአያቱ፣ በአፄ ኣድያም ሰገድ ኢያሱ ስም ተጠራ። ግብር በየቀኑ ገባ። ኢያሱ፣ በወጉ መሠረት በአርባ ቀኑ ክርስትና ተነሣ።
ኢያሱ ከተወለደ በኋላ፣ የመጀመሪያው መስቀል ነው። ለአፄ በካፋ ዓመታዊ ሠራዊት ግባት ከፍተኛ ዝግጅት እየተደረገ ነው። እንደ ጎጃምና ትግራይ ካሉ ራቅ ካሉ ግዛቶች የሚመጡ አስተዳዳሪ መኳንንት
ክረምቱ ሳይገባ ግንቦት ወር ላይ እያንዳንዳቸው ሠራዊታቸውን
ይዘው ጐንደር ሲገቡ፣ እንደ ስሜንና ቤገምድር ካሉ ቅርብ ቦታዎች የሚመጡት ደግሞ ዐዲስ ዓመትን ቤታቸው ውለው ሠራዊታቸውን ይዘው ጐንደር ገብተዋል። ቤተመንግሥት ዙርያ ለየግላቸውና ይዘውት
ለመጡት ሠራዊት ድንኳን ተተክሎላቸው እዚያው አርፈዋል።
ምንትዋብና አያቷ ስለ ሠራዊት ግባቱ አስፈላጊነት ሲነጋገሩ
አያትየው፣ ነገሥታቱ እኼን በዓል ሚያደርጉት አንድም እንግዲህ
ወታደራዊ ጉልበታቸውን ለማሳየት...” ብለው ሲጀምሩ አቋረጠቻቸው።
“ለማን ነው ሚያሳዩት?”
“ለሁሉም። እሱ ብቻ ማዶል። የመኳንንቱን ታማኝነት ለማረጋገጥም ሲሉ ነው። ሌላ ደሞ... ደንብ ሲያወጡ ወይም አዋጅ ሲነግሩ መኳንንቱ
በየግዛታቸው ያነን ደንብና አዋጅ በተመሳሳይ መንገድ እንዲያስከብሩ ጭምር ነው። ሌላው ደሞ መቸም ንጉሡ መኳንንቱ እንዳያምጹባቸው...
ተቀይመዋቸው ከሆነ ደሞ ለማረጋጋትና ሰላም ለመፍጠር በጋብቻ ሚተሳሰሩበትም ግዝየ ነው። በዝኸ ግዝየ አንድ የተቀየመ መኰንን አሞኛል ብሎ ሊቀር ይችላል። እናም እኼ ግዝየ ጃንሆይ አለ ነገር ሚሉበት፣ ብዙ ነገር ሚያውቁበትና ሚስተካከል ኻለም ተሎ ብለው ሚያስተካክሉበትም ግዝየ ነው” አሏት።
የበዓሉ ዕለት፣ ምንትዋብ ከአፄ በካፋ ጎን ድባብ ተይዞላት አደባባይ ወጣች። ሥርዐቱን ለማየት እጅግ ጓግታለች። ከንጉሠ ነገሥቱ ጎን ተቀመች። ጐንደሬዎችም ይህን ታላቅ በዓል ለመታደም ሥራቸውን
ነቅለው ወጥተዋል። ፎካሪዎች በየተራ እየወጡ ወደላይ ወደታች እያሉ ፎከሩ፣ ሽለሉ። ንጉሠ ነገሥቱን አወደሱ፤ አመሰገኑ።ሽለላውና ፉከራው ሲቆም፣ በአጋፋሪ መሪነት ታላቁ ስልፍ ተጀመረ።
👍13
ባለነፍጡ እንዲሁም ባለጦሩ ጋሻውን አንግቦ ወጣ። የበግ ለምዱን ትከሻው ላይ ጣል አድርጎ፣ ፀጉሩን አጎፍሮ በታላቅ ሥነ-ሥርዐትና ኩራት ጉልበቱንና ታማኝነቱን እያሳየ በንጉሠ ነገሥቱ፣ በመሣፍንቱ፣
በመኳንንቱና በሕዝቡ ፊት ተመመ። ሴቱ በዕልልታ ወንዱ በሆታ ተቀበላቸው፤ አከበራቸው፤ ተማመነባቸው፤ አድናቆቱን ገለፀላቸው።
ምንትዋብ፣ ከየቦታው በመጣው ጦር ብዛትና ሥርዐት ተደነቀች።
ንጉሠ ነገሥቱም የተሰማቸውን ደስታና ኩራት አስተዋለች።
ከሰልፉ በኋላ፣ በዓሉ ላይ የተገኘው ሁሉ ግብር ለመታደም ወደ ፋሲል ቤተመንግሥት ግቢ ግብር አዳራሽ አመራ። በሚቀጥሉት ቀናትም ንጉሠ ነገሥቱ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከመሣፍንቱና ከየግዛቱ ከመጡት መኳንንት ጋር ስለ ሃገር ደህንነት፣ ስለወሰን አጠባበቅ፣ ስለግብር አሰባሰብ የመሳሰሉ ጉዳዮች ላይ መከሩ። ከየግዛቱ የመጡት መኳንንትም መስቀልን አክብረው መስከረም መጨረሻ ላይ
ወደየመጡበት ተመለሱ።
እንደዚህ እያለም፣ ለምንትዋብ ዓለም ሙሉ ሆነችላት፣ ሕይወት
ዐዲስ ትርጉም ሰጠቻት። ተናግቶባት የነበረውን በራሷ መተማመንን መለሰችላት፤ ጥንካሬ አከለችላት። ቤተመንግሥት ውስጥ የሚኖራትን
ስፍራ እንድታመቻች በር ከፈተችላት። ቤተመንግሥትም ዓለምን በተለየ መልክ እንድትመለከት አደረጋት።
ውሉም እየሰፋላት መጣ።
የቤተመንግሥት ሕይወት በወግ የታጠረ፣ ያገር ጉዳይ የሚመከርበትና የሚወሰንበት፣ ጥሩም ክፉም የሚታለምበት፣ ሃይማኖታዊ ሆነ ሌላ
ወገናዊነት ጎልቶ የሚወጣበት፣ ለመሾም ለመሸለም ፉክክርና ሽኩቻ የበዛበት፣ በተለይም ደግሞ የቤተመንግሥቱ አንዱ ክፍል የሆነው መሠሪ የተባለው ድብቅ ቦታ ንጉሠ ነገሥቱ ከመሣፍንቱና ከመኳንንቱ ጋር እንደ ጦርነት ያለ ከፍተኛ የሃገር ጉዳይ የሚመክሩበት፣ ሤራ
የሚሸረብበትና የሚፈታበት፣ ውሳኔ የሚሰጥበትና ሹም ሽር የሚካሄድበት ቦታ መሆኑን አበጥራ አወቀች።
የቤተመንግሥት ወግና ውስብስብነት እንደበፊቱ ግራ ማጋባቱን ተወ።
ኢያሱን ከወለደች በኋላ፣ የቤተመንግሥት ብቻ ሳይሆን የሃገር ጉዳይ ላይ መወያየትና ማን መሾም ማን ደግሞ መሻር እንዳለበት ሐሳብ መስጠት ጀመረች።
ንጉሠ ነገሥቱም ቢሆኑ በአስተዋይነቷ ተመኩ፤ የሰዎችን ባህርይ ጠንቅቃ ማወቅ በመቻሏም ተደነቁ። ማታ ማታ መኝታ ቤት ከመግባታቸው በፊት ማምሻ ክፍል ውስጥ ተቀምጠው ከእሷ ጋር መወያየት የሚያስደስታቸው ነገር ሆኖ አገኙት።
አንድ ምሽት ላይ እዛው ማምሻ ክፍል ውስጥ ተቀምጠው ሲያወጉ፡“ጃንሆይ እንዳየሁት ጠላቶች አሉዎ” አለቻቸው፣ ብዙ ናቸው ከማለት ተቆጥባ።
ንግሥና ማለት እኼው ማዶል? ጠላት ማፍራት? እኼው ነው።
አንዱን ሹሜ ሌላውን ስሽር የተሻረው ያኮርፋል... ያምጣል። ግብር መገበር ያለበት ሲያዘገይ ወይም አልገብርም ሲል ስትቀጭው ጦር አስከትሎ ይነሳል። ርስት ነጥቆ የያዘውን እነጥቀዋለሁ፤ ይቀየመኛል።
ነፍስ አጥፍቶ ይፈረድበትና ይግባኝ ብሎ ይመጣል፤ ፍትሑ ለሟች ተኾነ የዳኞቹን ፍርድ አጸናበታለሁ። ያንየ ተወላጆቹ ያኮርፉኛል።ስለዝኸ ዳኝነት ወይም ንግሥ የሚወደዱበት ሥራ ማዶል፤ አይግረምሽ እናቴዋ።”
“መቸም ኻጤ አድያም ሰገድ ኢያሱ በኋላ፣ ኸነበሩት ጊዜያት ጋር ሲተያይ አሁን ይሻላል። ቢሆንም አንዳንዶች አይተኙልዎትም።
አመጠኛውን ሁሌ ኸመቅጣት በዘዴ መያዝ ጥሩ ነው።”
“ውነትሽ ነው። እኔም ሳልወድ በግድ ወደ ቅጣቱ አደላለሁ መሰል።ዛዲያ እኮ በጋብቻ እያስተሳሰርሁ፣ እየሾምሁ፣ አየሸለምሁ፣ መሬትና
ጉልት እየሰጠሁ ለማባበል ሞክራለሁ።”
“የኔም ዘመዶች እኮ ሊያግዙዎ ይችላሉ። የእሚታ ዮልያና ወንድም
ኒቆላዎስ የተማረና ብልህ ሰው ነው። በዕድሜም ብስል ነው። ቀኝ
እጅዎ... ኣማካሪዎ ሊሆን ይችላል። አጎቴ አርከሌድስም የተማረ ብቻ ሳይሆን ደፋርና ታማኝ ነው። ቤተመንግሥቱን ቀጥ አርጎ ይይዝልዎታል። ወንድሜ ወልደልዑልም ቢሆን ትምርት አለው። ላገር ሚበቃ ብርቱና አዋቂ ሰው ነው። እሽቴ፣ ነጮ፣ ጌታና አውሳቢዮስም ትምርት አላቸው ... ታዛዥ አገልጋይዎ እንጂ ሌላ አይሆኑም። እኒህ ሁሉ አጠገብዎ ኻሉ አለስጋት ሁሉን ማረግ ይችላሉ።”
“መልካም ብለሻል።”
“እንደማየው ካህናቱም አሁን ውስጥ ውስጡን ሽኩቻ ላይ ናቸው።እንደፊቶቹ ነገሥታት በአደባባይ ክርክር ቢያረጉ ያረጋጓቸው ነበር።ቅባቶቹ ክርክሩን ይፈልጉታል።”
“ቅባቶቹ ክርክሩን ይፈልጉታል” ስትል እሷ ወደቅባት ስለምታዘነብል አዝማሚያዋ ገባቸው።
“ክርክሩን ለማረግ አስቤያለሁ። ብቻ ቅባቶቹን አረጋጋለሁ ስል
ሌሎቹን ደሞ አስቀይማለሁ። ቅባቶቹን አረጋጋ ብየ አባቴ ያቆዩትን የተዋሕዶ ሃይማኖት እንዴት መጉዳት ይቻለኛል?”
“በክርክሩ ቅባቶች ኻቸነፉ መቸም... በወንድምዎ ባጤ ዳዊት ግዝየ አቸንፈው ማልነበር?”
“እሱ ብዙ ታሪክ አለው። ቅባቶች አቸነፉ ብየ ሃይማኖቴን መቀየር
አይቻለኝም። ቢስማሙልኝማ ሰላም አገኝ ነበር።”
“ውነትዎ ነው። ዋናው ነገር እኮ ሁሉም እንደ ሃይማኖቱ መሆኑ
ነው።”
“ሁሉ እንደሱ አያስብ ሁኖ ነው እንጂ እንደሱ ኻሰበማ ክርክር ምን ያረግ ኑሯል?”
ሁለቱም ዝም ብለው ቆዩና ወደ መኝታ ክፍላቸው ገቡ።
ብዙም ሳይቆዩ፣ ስለፍቅሯና ስለአስተዋይነቷ ሲሉ በዕድሜ የገፋውን ኒቆላዎስን ግራዝማችነት፣ አርከሌድስን የአሪንጎ አስተዳዳሪ በኋላም
የእልፍኝ አዛዥ በማለት ማዕረግ ሰጧቸው። ወልደልዑልን፣ እሽቴንና
የአጎቶቿን ልጆች የቤተመንግሥት ባለሟሎች አድርገው ሾሟቸው።
ምንትዋብ ቋረኞችን ቤተመንግሥት ውስጥ አደላደለች።
ከሁሉ በላይ ግን ኢያሱን መንከባከብ ቀዳሚ ተግባሯ ሆነ። ኢያሱ ሦስተኛ ዓመቱን ሲይዝ ከሌሎች ነጋሢያን ልጆች ጋር ግቢ ውስጥ ጨዋታ ሲጀምር፣ በካፋ
“ልዤን እንዳይገድሉብኝ” ብለው ስጋት ገባቸው። ምንትዋብ እንደ ሌሎች ነጋሢያን ልጆች ዘመድጋ ይላክብኛል ብላ ፈራች። ሰንበት ብሎ ኢያሱ፣ አፄ በካፋ ከሌላ የወለዷት እህቱ ውቢት ዘንድ መሄዱ ሲረጋገጥ ጭንቅ ዋጣት።
እንደ እሷ ፈቃድ ቢሆን አጠገቧ አድርጋ አያቷ እሷን በዕውቀትና
በግብረገብ አንጸው እንዳሳደጓት፣ ልጇን ልታስተምር፣ በመልካም
ምግባር ልታንጽና በአካል ልትገነባ ፈልጋ፣ ተመኝታና ተዘጋጅታ
የነበረው ሁሉ መና ሆኖ መቅረቱ አሳሰባት።
አንድ ምሽት ከራት በኋላ ነው። ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር ማምሻ ክፍል
ውስጥ ወንበሮቻቸው ላይ ቁጭ ብለው ይጫወታሉ። በካፋ ፈገግ አሉና፣
“ዛሬ ምንገድ ስኸድ አንዱ ደንጊያ ላይ ተቀምጦ ጠሐይ ይሞቃል። እኔ ስመጣ አልተነሣም” አሏት።
ወሬውን ለመንገር ካላቸው ጉጉት የተነሣ፣ ልቧ ከእሳቸው ጋር
እንዳልሆነና የወትሮው ፀሐይ የመሰለው ፊቷ ደመና እንደጣለበት አላስተዋሉም።
“ኒቆላዎስ ቆጣ ብሎ፣ “አንተ ንጉሥ ሲመጣ ማትነሳ?' ሲለው
ሰውየው፣ ንጉሥ መሆኑን በምን አውቃለሁ? ግንባሩ ላይ የለ። እኔ
ኸዝኸ ቁጭ ብየ ጠሐይ ስሞቅ ያከበርኩት የመሬቱን ሳይሆን የሰማዩን ንጉሥ ነው' ብሎ ሲመልስለት ተሳሳቅን...” ብለው አለመሳቋንና ፊቷ መለዋወጡን ልብ አሉና ደነገጡ።
“ምነው የኔ ዓለም የከፋሽ ትመስያለሽ? ላፍታ ስንኳ እንድትከፊብኝ አልሻም። የተከፋሽበት ነገር ካለ አዋዪኝ” አሏት።
“ጃንሆይ የኢያሱ ነገር ያሳስበኛል። እርሶ ውቢት ዘንድ ሽሬ
መስደድ ይፈልጋሉ። እኔ ደሞ ኸዝኸ ሁኖ ትምርቱን እንዲማር ነው እምሻ ። የቤተመንግሥትም ወግ እየተማረ ቢያድግ ነው ምመርጥ። ሌት ተቀን ሚያስጨንቀኝ፣ እንቅልፍ ሚነሳኝ እኼ ነው። ሌላ ቦታ ኸዶብኝ ተኝቼ ማደር አይሆንልኝም።”
በመኳንንቱና በሕዝቡ ፊት ተመመ። ሴቱ በዕልልታ ወንዱ በሆታ ተቀበላቸው፤ አከበራቸው፤ ተማመነባቸው፤ አድናቆቱን ገለፀላቸው።
ምንትዋብ፣ ከየቦታው በመጣው ጦር ብዛትና ሥርዐት ተደነቀች።
ንጉሠ ነገሥቱም የተሰማቸውን ደስታና ኩራት አስተዋለች።
ከሰልፉ በኋላ፣ በዓሉ ላይ የተገኘው ሁሉ ግብር ለመታደም ወደ ፋሲል ቤተመንግሥት ግቢ ግብር አዳራሽ አመራ። በሚቀጥሉት ቀናትም ንጉሠ ነገሥቱ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከመሣፍንቱና ከየግዛቱ ከመጡት መኳንንት ጋር ስለ ሃገር ደህንነት፣ ስለወሰን አጠባበቅ፣ ስለግብር አሰባሰብ የመሳሰሉ ጉዳዮች ላይ መከሩ። ከየግዛቱ የመጡት መኳንንትም መስቀልን አክብረው መስከረም መጨረሻ ላይ
ወደየመጡበት ተመለሱ።
እንደዚህ እያለም፣ ለምንትዋብ ዓለም ሙሉ ሆነችላት፣ ሕይወት
ዐዲስ ትርጉም ሰጠቻት። ተናግቶባት የነበረውን በራሷ መተማመንን መለሰችላት፤ ጥንካሬ አከለችላት። ቤተመንግሥት ውስጥ የሚኖራትን
ስፍራ እንድታመቻች በር ከፈተችላት። ቤተመንግሥትም ዓለምን በተለየ መልክ እንድትመለከት አደረጋት።
ውሉም እየሰፋላት መጣ።
የቤተመንግሥት ሕይወት በወግ የታጠረ፣ ያገር ጉዳይ የሚመከርበትና የሚወሰንበት፣ ጥሩም ክፉም የሚታለምበት፣ ሃይማኖታዊ ሆነ ሌላ
ወገናዊነት ጎልቶ የሚወጣበት፣ ለመሾም ለመሸለም ፉክክርና ሽኩቻ የበዛበት፣ በተለይም ደግሞ የቤተመንግሥቱ አንዱ ክፍል የሆነው መሠሪ የተባለው ድብቅ ቦታ ንጉሠ ነገሥቱ ከመሣፍንቱና ከመኳንንቱ ጋር እንደ ጦርነት ያለ ከፍተኛ የሃገር ጉዳይ የሚመክሩበት፣ ሤራ
የሚሸረብበትና የሚፈታበት፣ ውሳኔ የሚሰጥበትና ሹም ሽር የሚካሄድበት ቦታ መሆኑን አበጥራ አወቀች።
የቤተመንግሥት ወግና ውስብስብነት እንደበፊቱ ግራ ማጋባቱን ተወ።
ኢያሱን ከወለደች በኋላ፣ የቤተመንግሥት ብቻ ሳይሆን የሃገር ጉዳይ ላይ መወያየትና ማን መሾም ማን ደግሞ መሻር እንዳለበት ሐሳብ መስጠት ጀመረች።
ንጉሠ ነገሥቱም ቢሆኑ በአስተዋይነቷ ተመኩ፤ የሰዎችን ባህርይ ጠንቅቃ ማወቅ በመቻሏም ተደነቁ። ማታ ማታ መኝታ ቤት ከመግባታቸው በፊት ማምሻ ክፍል ውስጥ ተቀምጠው ከእሷ ጋር መወያየት የሚያስደስታቸው ነገር ሆኖ አገኙት።
አንድ ምሽት ላይ እዛው ማምሻ ክፍል ውስጥ ተቀምጠው ሲያወጉ፡“ጃንሆይ እንዳየሁት ጠላቶች አሉዎ” አለቻቸው፣ ብዙ ናቸው ከማለት ተቆጥባ።
ንግሥና ማለት እኼው ማዶል? ጠላት ማፍራት? እኼው ነው።
አንዱን ሹሜ ሌላውን ስሽር የተሻረው ያኮርፋል... ያምጣል። ግብር መገበር ያለበት ሲያዘገይ ወይም አልገብርም ሲል ስትቀጭው ጦር አስከትሎ ይነሳል። ርስት ነጥቆ የያዘውን እነጥቀዋለሁ፤ ይቀየመኛል።
ነፍስ አጥፍቶ ይፈረድበትና ይግባኝ ብሎ ይመጣል፤ ፍትሑ ለሟች ተኾነ የዳኞቹን ፍርድ አጸናበታለሁ። ያንየ ተወላጆቹ ያኮርፉኛል።ስለዝኸ ዳኝነት ወይም ንግሥ የሚወደዱበት ሥራ ማዶል፤ አይግረምሽ እናቴዋ።”
“መቸም ኻጤ አድያም ሰገድ ኢያሱ በኋላ፣ ኸነበሩት ጊዜያት ጋር ሲተያይ አሁን ይሻላል። ቢሆንም አንዳንዶች አይተኙልዎትም።
አመጠኛውን ሁሌ ኸመቅጣት በዘዴ መያዝ ጥሩ ነው።”
“ውነትሽ ነው። እኔም ሳልወድ በግድ ወደ ቅጣቱ አደላለሁ መሰል።ዛዲያ እኮ በጋብቻ እያስተሳሰርሁ፣ እየሾምሁ፣ አየሸለምሁ፣ መሬትና
ጉልት እየሰጠሁ ለማባበል ሞክራለሁ።”
“የኔም ዘመዶች እኮ ሊያግዙዎ ይችላሉ። የእሚታ ዮልያና ወንድም
ኒቆላዎስ የተማረና ብልህ ሰው ነው። በዕድሜም ብስል ነው። ቀኝ
እጅዎ... ኣማካሪዎ ሊሆን ይችላል። አጎቴ አርከሌድስም የተማረ ብቻ ሳይሆን ደፋርና ታማኝ ነው። ቤተመንግሥቱን ቀጥ አርጎ ይይዝልዎታል። ወንድሜ ወልደልዑልም ቢሆን ትምርት አለው። ላገር ሚበቃ ብርቱና አዋቂ ሰው ነው። እሽቴ፣ ነጮ፣ ጌታና አውሳቢዮስም ትምርት አላቸው ... ታዛዥ አገልጋይዎ እንጂ ሌላ አይሆኑም። እኒህ ሁሉ አጠገብዎ ኻሉ አለስጋት ሁሉን ማረግ ይችላሉ።”
“መልካም ብለሻል።”
“እንደማየው ካህናቱም አሁን ውስጥ ውስጡን ሽኩቻ ላይ ናቸው።እንደፊቶቹ ነገሥታት በአደባባይ ክርክር ቢያረጉ ያረጋጓቸው ነበር።ቅባቶቹ ክርክሩን ይፈልጉታል።”
“ቅባቶቹ ክርክሩን ይፈልጉታል” ስትል እሷ ወደቅባት ስለምታዘነብል አዝማሚያዋ ገባቸው።
“ክርክሩን ለማረግ አስቤያለሁ። ብቻ ቅባቶቹን አረጋጋለሁ ስል
ሌሎቹን ደሞ አስቀይማለሁ። ቅባቶቹን አረጋጋ ብየ አባቴ ያቆዩትን የተዋሕዶ ሃይማኖት እንዴት መጉዳት ይቻለኛል?”
“በክርክሩ ቅባቶች ኻቸነፉ መቸም... በወንድምዎ ባጤ ዳዊት ግዝየ አቸንፈው ማልነበር?”
“እሱ ብዙ ታሪክ አለው። ቅባቶች አቸነፉ ብየ ሃይማኖቴን መቀየር
አይቻለኝም። ቢስማሙልኝማ ሰላም አገኝ ነበር።”
“ውነትዎ ነው። ዋናው ነገር እኮ ሁሉም እንደ ሃይማኖቱ መሆኑ
ነው።”
“ሁሉ እንደሱ አያስብ ሁኖ ነው እንጂ እንደሱ ኻሰበማ ክርክር ምን ያረግ ኑሯል?”
ሁለቱም ዝም ብለው ቆዩና ወደ መኝታ ክፍላቸው ገቡ።
ብዙም ሳይቆዩ፣ ስለፍቅሯና ስለአስተዋይነቷ ሲሉ በዕድሜ የገፋውን ኒቆላዎስን ግራዝማችነት፣ አርከሌድስን የአሪንጎ አስተዳዳሪ በኋላም
የእልፍኝ አዛዥ በማለት ማዕረግ ሰጧቸው። ወልደልዑልን፣ እሽቴንና
የአጎቶቿን ልጆች የቤተመንግሥት ባለሟሎች አድርገው ሾሟቸው።
ምንትዋብ ቋረኞችን ቤተመንግሥት ውስጥ አደላደለች።
ከሁሉ በላይ ግን ኢያሱን መንከባከብ ቀዳሚ ተግባሯ ሆነ። ኢያሱ ሦስተኛ ዓመቱን ሲይዝ ከሌሎች ነጋሢያን ልጆች ጋር ግቢ ውስጥ ጨዋታ ሲጀምር፣ በካፋ
“ልዤን እንዳይገድሉብኝ” ብለው ስጋት ገባቸው። ምንትዋብ እንደ ሌሎች ነጋሢያን ልጆች ዘመድጋ ይላክብኛል ብላ ፈራች። ሰንበት ብሎ ኢያሱ፣ አፄ በካፋ ከሌላ የወለዷት እህቱ ውቢት ዘንድ መሄዱ ሲረጋገጥ ጭንቅ ዋጣት።
እንደ እሷ ፈቃድ ቢሆን አጠገቧ አድርጋ አያቷ እሷን በዕውቀትና
በግብረገብ አንጸው እንዳሳደጓት፣ ልጇን ልታስተምር፣ በመልካም
ምግባር ልታንጽና በአካል ልትገነባ ፈልጋ፣ ተመኝታና ተዘጋጅታ
የነበረው ሁሉ መና ሆኖ መቅረቱ አሳሰባት።
አንድ ምሽት ከራት በኋላ ነው። ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር ማምሻ ክፍል
ውስጥ ወንበሮቻቸው ላይ ቁጭ ብለው ይጫወታሉ። በካፋ ፈገግ አሉና፣
“ዛሬ ምንገድ ስኸድ አንዱ ደንጊያ ላይ ተቀምጦ ጠሐይ ይሞቃል። እኔ ስመጣ አልተነሣም” አሏት።
ወሬውን ለመንገር ካላቸው ጉጉት የተነሣ፣ ልቧ ከእሳቸው ጋር
እንዳልሆነና የወትሮው ፀሐይ የመሰለው ፊቷ ደመና እንደጣለበት አላስተዋሉም።
“ኒቆላዎስ ቆጣ ብሎ፣ “አንተ ንጉሥ ሲመጣ ማትነሳ?' ሲለው
ሰውየው፣ ንጉሥ መሆኑን በምን አውቃለሁ? ግንባሩ ላይ የለ። እኔ
ኸዝኸ ቁጭ ብየ ጠሐይ ስሞቅ ያከበርኩት የመሬቱን ሳይሆን የሰማዩን ንጉሥ ነው' ብሎ ሲመልስለት ተሳሳቅን...” ብለው አለመሳቋንና ፊቷ መለዋወጡን ልብ አሉና ደነገጡ።
“ምነው የኔ ዓለም የከፋሽ ትመስያለሽ? ላፍታ ስንኳ እንድትከፊብኝ አልሻም። የተከፋሽበት ነገር ካለ አዋዪኝ” አሏት።
“ጃንሆይ የኢያሱ ነገር ያሳስበኛል። እርሶ ውቢት ዘንድ ሽሬ
መስደድ ይፈልጋሉ። እኔ ደሞ ኸዝኸ ሁኖ ትምርቱን እንዲማር ነው እምሻ ። የቤተመንግሥትም ወግ እየተማረ ቢያድግ ነው ምመርጥ። ሌት ተቀን ሚያስጨንቀኝ፣ እንቅልፍ ሚነሳኝ እኼ ነው። ሌላ ቦታ ኸዶብኝ ተኝቼ ማደር አይሆንልኝም።”
👍15❤1
የፊቷን መከስከስና የድምጿን መርበትበት አስተውለው ልባቸው
ተነካ።
“የኔ ዓለም...” ብለው እጇን ሳብ አድርገው እያሻሹ፣ምንትዋብ... ኻላንቺ መኖር እንደማልችለው ሁሉ ኸልዤ ተነጥዬ መኖር አይቻለኝም። ወድጄ ማዶል ኻይኔ ርቆ እንዲኸድ ምፈልገው። እንደምታቂው ብዙ ጠላቶች አሉኝ። እኔን ለመበቀል ሲሉ ይገድሉብኛል ብየ ሰግቸ ነው። ኸገደሉት እኮ አንቺም ብትሆኚ
ታዝኝብኛለሽ። ባክሽ ተረጂኝ። ትምርትም ቢሆን ኸዛው ይማራል።ኪዳነ ምሕረት ትርዳኝ፣ ተሎ እንዲመለስ አረጋለሁ” ብለው፣ የእሳቸው ጭንቀት ቢጨምርም የእሷን ሊያቃልሉ ሞከሩ።
ሊደብቁት ያልቻሉትን መጨነቅ ፊታቸው ላይ አየች። እሷን
በማስደሰትና የልጃቸውን ሕይወት ለማዳን በመፈለግ ልባቸው እንደተከፈለ ተረዳች። አንጀቷ ተላወሰ። የጠየቅሁትን ሁሉ
ይፈጥሙልኛል። እኼ ኢያሱን አደጋ ላይ ሚጥል ጉዳይ ስለሆነ
ልረዳቸው ይገባል አለች፣ ለራሷ።
ጭንቀታቸውን ለማቃለልም፣ “ውነትዎ ነው። ልዣችን አደጋ ላይ
ሲወድቅ ማየት አልፈልግም። ይኸድ ግድ የለም” አለቻቸው።
ኢያሱ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ እህቱጋ ሽሬ ተላከ። ምንትዋብ
እንባዋን ረጨች። በናፍቆት ባባች።ልጇ አጠገቧ ባለመኖሩና ያሰበችለትን ሁሉ ማድረግ ባለመቻሏ ቅር ተሰኘች። አያቷ ቋራ ሄደው ከእናቷ ጋር ተመልሰው መጥተው አጠገቧ ቢሆኑም፣ ከልጇ ጋር በመለያየቷ ምክንያት የተፈጠረውን ክፍት ቦታ ሊሞሉ አቃታቸው። ቀደም ብሎ ከአፄ በካፋ የደጃዝማችነት
ማዕረግ አግኝተው የነበሩት አባቷ በቅርቡ አርፈው ስለነበር የእሳቸው
ሐዘን ተጨምሮበት ነገሩን አባባሰው። ከእናቷና ከአያቷ ጋር ስትሆን በአመዛኙ የምታወራው ስለ ልጇ በመሆኑ ጨርሰው ሊያጽናኗት አልሆንላቸው አለ።
አንድ ቀን፣ እናቷ ወሬ ለመቀየር ብለው ጥላዬ ከቤት ጠፍቶ በመሄዱ ባላምባራስ ሁነኝ፣ “ልጄን አማርሬ እንዲጠፋ አረግሁት” ብለው በሐዘን ብዛት እንደሞቱ ነገሯት።
“ጥላዬ የት ጠፋ?” አለቻቸው፣ ደንግጣ።
“ማን አወቀ። አንቺ ረቡዕ ወደዝኽ ልትነሺ ማክሰኞ ነው አሉ
የጠፋው። ጌጤ አንቺን ልትሰናበትሽ ስንኳ አልመጣችም፤ እቷጋ ይሆናል ብላ ልትፈልገው ኸዳ። መቸም ሰው ትሆናለች አላልንም ነበር፤ እኼው አለች። እንጃ ዐይኗ በልቅሶ ሳይጠፋም ኣይቀር። እኼው እስተዛሬ የት እንደደረሰ ማንም አላወቀ” አሏት።
ምንትዋብ፣ ደነገጠች፤ አዘነች፤ ልትናገር ፈልጋ ልሳኗ ተዘጋ።
የእሷን መሄድ ተከትሎ መጥፋቱ ገረማት። ለቀናት፣ “የት ኸዶ ይሆን?” የሚለው ጥያቄ ለልጇ ያላት ጭንቀት ላይ ተደምሮ ልቧን አስጨነቀው።......
✨ይቀጥላል✨
ተነካ።
“የኔ ዓለም...” ብለው እጇን ሳብ አድርገው እያሻሹ፣ምንትዋብ... ኻላንቺ መኖር እንደማልችለው ሁሉ ኸልዤ ተነጥዬ መኖር አይቻለኝም። ወድጄ ማዶል ኻይኔ ርቆ እንዲኸድ ምፈልገው። እንደምታቂው ብዙ ጠላቶች አሉኝ። እኔን ለመበቀል ሲሉ ይገድሉብኛል ብየ ሰግቸ ነው። ኸገደሉት እኮ አንቺም ብትሆኚ
ታዝኝብኛለሽ። ባክሽ ተረጂኝ። ትምርትም ቢሆን ኸዛው ይማራል።ኪዳነ ምሕረት ትርዳኝ፣ ተሎ እንዲመለስ አረጋለሁ” ብለው፣ የእሳቸው ጭንቀት ቢጨምርም የእሷን ሊያቃልሉ ሞከሩ።
ሊደብቁት ያልቻሉትን መጨነቅ ፊታቸው ላይ አየች። እሷን
በማስደሰትና የልጃቸውን ሕይወት ለማዳን በመፈለግ ልባቸው እንደተከፈለ ተረዳች። አንጀቷ ተላወሰ። የጠየቅሁትን ሁሉ
ይፈጥሙልኛል። እኼ ኢያሱን አደጋ ላይ ሚጥል ጉዳይ ስለሆነ
ልረዳቸው ይገባል አለች፣ ለራሷ።
ጭንቀታቸውን ለማቃለልም፣ “ውነትዎ ነው። ልዣችን አደጋ ላይ
ሲወድቅ ማየት አልፈልግም። ይኸድ ግድ የለም” አለቻቸው።
ኢያሱ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ እህቱጋ ሽሬ ተላከ። ምንትዋብ
እንባዋን ረጨች። በናፍቆት ባባች።ልጇ አጠገቧ ባለመኖሩና ያሰበችለትን ሁሉ ማድረግ ባለመቻሏ ቅር ተሰኘች። አያቷ ቋራ ሄደው ከእናቷ ጋር ተመልሰው መጥተው አጠገቧ ቢሆኑም፣ ከልጇ ጋር በመለያየቷ ምክንያት የተፈጠረውን ክፍት ቦታ ሊሞሉ አቃታቸው። ቀደም ብሎ ከአፄ በካፋ የደጃዝማችነት
ማዕረግ አግኝተው የነበሩት አባቷ በቅርቡ አርፈው ስለነበር የእሳቸው
ሐዘን ተጨምሮበት ነገሩን አባባሰው። ከእናቷና ከአያቷ ጋር ስትሆን በአመዛኙ የምታወራው ስለ ልጇ በመሆኑ ጨርሰው ሊያጽናኗት አልሆንላቸው አለ።
አንድ ቀን፣ እናቷ ወሬ ለመቀየር ብለው ጥላዬ ከቤት ጠፍቶ በመሄዱ ባላምባራስ ሁነኝ፣ “ልጄን አማርሬ እንዲጠፋ አረግሁት” ብለው በሐዘን ብዛት እንደሞቱ ነገሯት።
“ጥላዬ የት ጠፋ?” አለቻቸው፣ ደንግጣ።
“ማን አወቀ። አንቺ ረቡዕ ወደዝኽ ልትነሺ ማክሰኞ ነው አሉ
የጠፋው። ጌጤ አንቺን ልትሰናበትሽ ስንኳ አልመጣችም፤ እቷጋ ይሆናል ብላ ልትፈልገው ኸዳ። መቸም ሰው ትሆናለች አላልንም ነበር፤ እኼው አለች። እንጃ ዐይኗ በልቅሶ ሳይጠፋም ኣይቀር። እኼው እስተዛሬ የት እንደደረሰ ማንም አላወቀ” አሏት።
ምንትዋብ፣ ደነገጠች፤ አዘነች፤ ልትናገር ፈልጋ ልሳኗ ተዘጋ።
የእሷን መሄድ ተከትሎ መጥፋቱ ገረማት። ለቀናት፣ “የት ኸዶ ይሆን?” የሚለው ጥያቄ ለልጇ ያላት ጭንቀት ላይ ተደምሮ ልቧን አስጨነቀው።......
✨ይቀጥላል✨
👍5❤1
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...በድሉ አሽናፊና ማንደፍሮ ጌጤነህ ቀድሞም ይተዋወቁ ነበር፡፡ መነሻው በድሉ የተሽከርካሪ ባለ ንብረት፣ ማንደፍሮ ሾፌር ስለሆነ ከህዝብ ማመላለስ ስራ
ጋር በተያያዘ በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ስለሚገናኙ ነበር::ከቅርብ ቀናት ወዲህ ደግሞ የተለየ ግንኙነት ፈጥረው ሰንብተዋል ማንደፍሮ ቀድሞ ይዞቶ
የነበረውን ተሽከርካሪ ትቶ በሌላ መኪና ላይ ለመቀጠር ሲፈልግ፣ በድሉ ደግሞ የአንድ ተሸከርካሪን ነባር ሾፌር አባርሮ ሌላ ለመቅጠር በነበረው ፍላጎት መሰረት
በመጠያየቃቸው ነው፡፡ በመጨረሻም ሁለት በቀጣሪና በተቀጣሪነት ስምምነት ላይ
ደርሰው ውል የተፈራረሙ ዕለት እማኝ ምስክሮቻቸውን ሲጋብዙ በዋሉበት ቀን ወደ ማታ ላይ ደግሞ ብቻቸውን ከአንድ ቡና ቤት ውስጥ ቁጭ ብለው ይጫወታሉ፡፡ በመሀል የደመወዝ ነገር ተነስቶ ቀድሞም ቢሆን ቅር ብሎት የነበረው ማንደፍሮ ስሜቱን ለበድሉ ማካፈል ጀመረ፡፡
የምትከፍለኝ ደመወዝ ከስራውና ከጣልክብኝ አደራ ጋር በፍጹም
አይጣጣምም::» አለው በድሉን፡፡
“ለዚህም እኔ ስለሆንኩ ነው ! አባቴ ቢሰማ 'ኡ ኡ' ነው የሚለውኑ ቀድሞ ስራው የታለና ከዚህ በላይ ደመወዝ ይከፈላል፡፡» ሲል በድሉ መለሰለት።
እውነቴን ነው በድሉ! እኔ ወደ ዲላ ጠጋ ለማለት የፈለኩበት ጉዳይ
ባይኖረኝ ኖሮ በዚህ ደሞዝ » ብሎ ሳይጨርስ በድሉ ቀደመው»
«ተጠቃለህ ብትገባማ ጥሩ»
«የሚቀር አልመሰለኝም፡፡»
«ቤት ልትሰራ አሰብክ?»
«መሰረቱን ጥያለሁ፡፡» አለ ማንደፍሮ ሳቅ እያለ በድሉን በማየት፡
«የት ቀበሌ»
«እዚህ ዜሮ አምስት ቀበሌ ስምንተኛ መንገድ አካባቢ
«እዚያ አካባቢ ክፍት ቦታ የታለና» አለና በድሉ የት ጋ ሊሆን
እንደሚችል ሲያሰላስል «ኪስ ቦታ አግኝቼ፡፡» በማለት ማንደፍሮ አሁንም ፈገግ እያለ በድለን ያየው ጀመር። በውስጡ ሌላ ምስጢር እንዳለ ከፊቱ ላይ ይነበባል።
«እኔ እንጃ!» አለና በድሉ ቢራውን ሊጎነጭ ብድግ እያረገ ገዝተህ እንደሆነ እንጂ በምሪት የሚሰጥ ቦታ እዚያ አካባቢ ስለመኖሩ ተጠራጠርኩ፡፡» አለው፡፡
«ለመሆኑ ያን አካባቢ በደንብ ታውቀዋለህ እንዴ?»
«ዲላ ውስጥ የማላውቀው ሰውና ቦታ የለም፡፡ አለና በድሉ ቢራውን
እየተጎነጨ «ግዛቴ አይደል?» በማለት ቀለደ፡፡
«እዚያ አካባቢ ማን ማን ታውቃለህ?»
«እኔ ከምዘረዝር አንተ እገሌ በለኛ»
«አንዲት መምህር ታውቃለህ?»
በድሉ ሽዋዬ ትዝ አለችው፡፡ ፈገግ ብሎ ማንደፍሮን ትኩር ብሎ
ከተመለከተ በኋላ ሽዋዬን እንዳይሆን?» አለው።
ማንደፍሮ እንደገና ድንግጥ አለና «እንዴ! እውነትም ታውቃታለህ እንዴ» ሲል ጠየቀው።
ሁለቱም በፈገግታ ተያዩና በተለይ በድሉ ሃሃሃሃ …ብሎ እየሳቀ «በደንብ አውቃታለሁ አለው።
«በምን ሁኔታ?» አለ ማንደፍሮም የባሰ እየደነገጠ።
«አይዞህ! ጉዳይ ካለህም አትደንግጥ። አንተ የጣልከውን መሰረት በማያነቃንቅ ሁኔታ ነው የማውቃት፡፡»
ሁስቱም ተሳሳቁ፡፡
«ለመሆኑ መቼ ጀምረህ ነው የምታውቃት?» ሲል በድሉ ማንደፍሮን ጠየቀው።
«ከዓመት አለፈኝ»
በድሉ በርናባስ ወደ ውጭ የሄደበትን ጊዜ አሰላስለና እሱ ከሄደ በኋላ፣ ግን ደግሞ ወዲያው እንደሄደ ሊሆን እንደሚችል ገምቶ በመገረም ዓይነት ራሱን ወዘወዘ።
«ምነው በድሉ? ተደርቤ ይሆን ወይስ…» ብሎ ማንደፍሮ በድሉን ትኩር ብሎ ሲያየው በድሉ ቀጠለ፡፡
«አይ አይ! እሱንማ ነገርኩህ! እኔ የማውቀው ሌላ ነገር ስላለ ያ ትዝ
ብሎኝ ነው:: አለው አሁንም ቢራውን እየተጎነጨ።
«መጥፎ ነገር ካለ ንገረኝ፡፡»
"ምንም እንዲያውም ለኔም ለአንተም ጥሩ አጋጣሚ ሳይሆን አይቀርም፡፡
«ልቤን አንጠለጠልከው»
“እንዴያውም እንዲህ አድርግ» አለ በድሉ ፈገግ ብሎ እያየው
«እንዴት?»
«የኔንና የአንተን ግኑኝነት ሳትነግራት አንድን ይቀንሳል ከሰው ጋር አስተዋውቅሻለው ተዘጋጂ! ብለህ የእሷንም ልብ አንጠልጥላጠው፡፡ አብረን እንሂድና የሚሆነውን ታያለህ።»
«ተው አንተ ሰው ደግሞ ከገባህ በኋላ አልወጣም ያልክ እንደሆንስ?»በማለት ማንደፍሮ ራሱ ስቆ በድሉንም አሳቀው።
እንዲህ እንዲህ እያሉ ሲጨዋወቱ አመሹ፡፡ በድሉ ግን ለማንደፍሮ
አንዳች ምስጢር አውጥቶ አልነገረውም፡፡ በባርናባስ ምትክ ማንደፍሮ በሸዋዬ ቤት መግባቱ ለበድሉ ጉዳዩ አልነበረም። ምክንያቱ ባርናባስ ባለ ትዳር መሆንና ከአንድ ዓመት በላይ ለሆነ ጊዜ ሊቆይ መቻሉ ሌላው ነው፡፡ ከዚያም በላይ ቀድሞ ነገር
በድሉና ባርናባስ ለረጅም ጊዜ የሚተዋወቁ የአንድ ከተማ ነዋሪዎች ከመሆናቸው በቀር የተለየ ግንኙነት አልነበራቸውም፡፡ ስለዚህም ከማንደፍሮ ጋር በሸዋዬ ቤት ከመገኘቱ ለእሶም ሆነ ለእሷ የሚጎረብጣቸው ነገር እንደሌለ ያውቃል፡፡
ማንደፍሮ የበድሉና የሸዋዬ መተዋወቅ መሰረቱ ምን ሊሆን እንደሚችልም ለማወቅ ሲጓጓ ሰንብቶ አንድ ቀን ከሄደበት አገር ዶሮ፣ ሽንኩርትና ቅቤ ገዝቶ በመምጣት ለሽዋዬ እያስረከበ በነገው ዕለት ትልቅ እንግዳ ጠርቻለሁ፡፡ ከአንቺም ጋር አስተዋውቃችኋለሁ :: ሴትነትሽ ይታይበታልና አስማምሪው፡፡» አላት፡፡
ማግስቱ ቅዳሜ ነው። ወደ አሥር ሠዓት አካባቢ ሸዋዬ በሁሉም ነገር ተዘጋጅታ የማንደፍርንና የትልቁን እንግዳ መምጣት ስትጠባበቅ ማንደፍሮ ከዲላ
ይርጋለም የነበረውን የደርሶ መልስ ምድብ ስራውን አጠናቆ ከበድሉ ጋር ለማምሻ የሚበቃ ጫት ገዝተው ከሸዋዬ ቤት ከች አሉ፡፡
«እንዴ!» አለች ሸዋዬ ደስታ አይሉት ድንጋጤ አንዳች የማታውቀው ስሜት መንፈሷን ልውጥውጥ እያደረገው። ቀጥላም «አንተ ነህ እንዴ ትልቁ እንግዳ!» አለችው በድሉን ልትስመው ጠጋ እያለች።
«በአንድ ወቅት ትልቅ ነበርን፡፡ እያደር ግን…» ብሎ በድሉ ሳቅ እያለ ሸዋዪን ሲስም ማንድፍሮ ጣልቃ ገባ::
«እንተዋወቅ ነበር እንዳትለ!»
«በአንተ ቤት ገና ማስተዋወቅህ ነው!» አለችና ሸዋዬ ሁለቱም ቁጭ እንዲሉ ጋበዘቻቸው::
«ተሽውደሀል ማንዴ።» አለው በድሉ ከተነጠፈው ፍራሽ ላይ ቁጭ እያለ::
«እንዴት?» አለ ማንደፍሮ የተገረመ በመምሰል።
«ቁጫ በልና በእርጋታ ይነገርሃል።» አለው በድሉ።
«ጉድ ሳይሰሙ መስከረም አይጠባም አሉ» እያለ ማንደፍሮም ወደ ፍራሻ
አለፍ ብሎ ተቀመጠና «የሸዋ፣ በይ ከጫት በፊት የሚበላ ነገር ቶሎ በይ!» አላት።
ሸዋዬም ግርምቷን ደጋግማ እየገለጸች ምግብ የማቅረብ ስራዋን ተያያዘችው:: በድሉ ከዚያ ቤት ከቀረ ከዓመት በላይ ሆኖታል፡፡ በሽዋዬ ቤት ያየው
ለውጥ እስገረመው። የሽዋዬ ታጣፊ አልጋ ልዩ በሆነ ሞዝቦልድ አልጋ ተተክታለች፣ ለብቻ ቢተኙበት
'የሰው ያለህ' የሚያሰኝ፡፡ ከፊትለፊቱ ባለ መስታወት
ብፌ ግድግዳ ጥግ ይዞ ተሰይሟል። የጓዳው በር እንኳ መጋረጃው ዓይን ይስባል።
ቤቱ በሮዝ ቀለም ተቀብቶ ፍክት ብሏል። ሁሉመሰ ነገር ደስ ይላል። ይህን ሁሉ ሲያጤን ቆይቶ የሸዋዬን ጓዳ ውስጥ መሆን አጋጣሚ በመጠቀም ወደ ማንደፍሮ ጆሮ ጠጋ በማለት በሹክሹታ አነጋገር «ምን መሰረት ጥያለሁ ትላለህ ዋልታውንም
አቁምሃል እንጂ» አለና ለራሱ እየሳቀ ማንደፍሮንም አሳቀው።
ሽዋዬ እንጀራና ወጡን ለበድሉና ለማንደፍሮ አቅርባ እየጋበዘች እሷ ግን የቡና ማፍላቱን ስራ ቀጠለች፡፡ ግን ከእነሱ ይበልጥ እሷ ነበረች የምትበላው ሁለቱም እየተፈራረቁ በሚያጎርሷት ጉርሻ ጉንጯ እየሞላ ስራ ያለማቋረጧ ደግሞ ለቡናው
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
...በድሉ አሽናፊና ማንደፍሮ ጌጤነህ ቀድሞም ይተዋወቁ ነበር፡፡ መነሻው በድሉ የተሽከርካሪ ባለ ንብረት፣ ማንደፍሮ ሾፌር ስለሆነ ከህዝብ ማመላለስ ስራ
ጋር በተያያዘ በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ስለሚገናኙ ነበር::ከቅርብ ቀናት ወዲህ ደግሞ የተለየ ግንኙነት ፈጥረው ሰንብተዋል ማንደፍሮ ቀድሞ ይዞቶ
የነበረውን ተሽከርካሪ ትቶ በሌላ መኪና ላይ ለመቀጠር ሲፈልግ፣ በድሉ ደግሞ የአንድ ተሸከርካሪን ነባር ሾፌር አባርሮ ሌላ ለመቅጠር በነበረው ፍላጎት መሰረት
በመጠያየቃቸው ነው፡፡ በመጨረሻም ሁለት በቀጣሪና በተቀጣሪነት ስምምነት ላይ
ደርሰው ውል የተፈራረሙ ዕለት እማኝ ምስክሮቻቸውን ሲጋብዙ በዋሉበት ቀን ወደ ማታ ላይ ደግሞ ብቻቸውን ከአንድ ቡና ቤት ውስጥ ቁጭ ብለው ይጫወታሉ፡፡ በመሀል የደመወዝ ነገር ተነስቶ ቀድሞም ቢሆን ቅር ብሎት የነበረው ማንደፍሮ ስሜቱን ለበድሉ ማካፈል ጀመረ፡፡
የምትከፍለኝ ደመወዝ ከስራውና ከጣልክብኝ አደራ ጋር በፍጹም
አይጣጣምም::» አለው በድሉን፡፡
“ለዚህም እኔ ስለሆንኩ ነው ! አባቴ ቢሰማ 'ኡ ኡ' ነው የሚለውኑ ቀድሞ ስራው የታለና ከዚህ በላይ ደመወዝ ይከፈላል፡፡» ሲል በድሉ መለሰለት።
እውነቴን ነው በድሉ! እኔ ወደ ዲላ ጠጋ ለማለት የፈለኩበት ጉዳይ
ባይኖረኝ ኖሮ በዚህ ደሞዝ » ብሎ ሳይጨርስ በድሉ ቀደመው»
«ተጠቃለህ ብትገባማ ጥሩ»
«የሚቀር አልመሰለኝም፡፡»
«ቤት ልትሰራ አሰብክ?»
«መሰረቱን ጥያለሁ፡፡» አለ ማንደፍሮ ሳቅ እያለ በድሉን በማየት፡
«የት ቀበሌ»
«እዚህ ዜሮ አምስት ቀበሌ ስምንተኛ መንገድ አካባቢ
«እዚያ አካባቢ ክፍት ቦታ የታለና» አለና በድሉ የት ጋ ሊሆን
እንደሚችል ሲያሰላስል «ኪስ ቦታ አግኝቼ፡፡» በማለት ማንደፍሮ አሁንም ፈገግ እያለ በድለን ያየው ጀመር። በውስጡ ሌላ ምስጢር እንዳለ ከፊቱ ላይ ይነበባል።
«እኔ እንጃ!» አለና በድሉ ቢራውን ሊጎነጭ ብድግ እያረገ ገዝተህ እንደሆነ እንጂ በምሪት የሚሰጥ ቦታ እዚያ አካባቢ ስለመኖሩ ተጠራጠርኩ፡፡» አለው፡፡
«ለመሆኑ ያን አካባቢ በደንብ ታውቀዋለህ እንዴ?»
«ዲላ ውስጥ የማላውቀው ሰውና ቦታ የለም፡፡ አለና በድሉ ቢራውን
እየተጎነጨ «ግዛቴ አይደል?» በማለት ቀለደ፡፡
«እዚያ አካባቢ ማን ማን ታውቃለህ?»
«እኔ ከምዘረዝር አንተ እገሌ በለኛ»
«አንዲት መምህር ታውቃለህ?»
በድሉ ሽዋዬ ትዝ አለችው፡፡ ፈገግ ብሎ ማንደፍሮን ትኩር ብሎ
ከተመለከተ በኋላ ሽዋዬን እንዳይሆን?» አለው።
ማንደፍሮ እንደገና ድንግጥ አለና «እንዴ! እውነትም ታውቃታለህ እንዴ» ሲል ጠየቀው።
ሁለቱም በፈገግታ ተያዩና በተለይ በድሉ ሃሃሃሃ …ብሎ እየሳቀ «በደንብ አውቃታለሁ አለው።
«በምን ሁኔታ?» አለ ማንደፍሮም የባሰ እየደነገጠ።
«አይዞህ! ጉዳይ ካለህም አትደንግጥ። አንተ የጣልከውን መሰረት በማያነቃንቅ ሁኔታ ነው የማውቃት፡፡»
ሁስቱም ተሳሳቁ፡፡
«ለመሆኑ መቼ ጀምረህ ነው የምታውቃት?» ሲል በድሉ ማንደፍሮን ጠየቀው።
«ከዓመት አለፈኝ»
በድሉ በርናባስ ወደ ውጭ የሄደበትን ጊዜ አሰላስለና እሱ ከሄደ በኋላ፣ ግን ደግሞ ወዲያው እንደሄደ ሊሆን እንደሚችል ገምቶ በመገረም ዓይነት ራሱን ወዘወዘ።
«ምነው በድሉ? ተደርቤ ይሆን ወይስ…» ብሎ ማንደፍሮ በድሉን ትኩር ብሎ ሲያየው በድሉ ቀጠለ፡፡
«አይ አይ! እሱንማ ነገርኩህ! እኔ የማውቀው ሌላ ነገር ስላለ ያ ትዝ
ብሎኝ ነው:: አለው አሁንም ቢራውን እየተጎነጨ።
«መጥፎ ነገር ካለ ንገረኝ፡፡»
"ምንም እንዲያውም ለኔም ለአንተም ጥሩ አጋጣሚ ሳይሆን አይቀርም፡፡
«ልቤን አንጠለጠልከው»
“እንዴያውም እንዲህ አድርግ» አለ በድሉ ፈገግ ብሎ እያየው
«እንዴት?»
«የኔንና የአንተን ግኑኝነት ሳትነግራት አንድን ይቀንሳል ከሰው ጋር አስተዋውቅሻለው ተዘጋጂ! ብለህ የእሷንም ልብ አንጠልጥላጠው፡፡ አብረን እንሂድና የሚሆነውን ታያለህ።»
«ተው አንተ ሰው ደግሞ ከገባህ በኋላ አልወጣም ያልክ እንደሆንስ?»በማለት ማንደፍሮ ራሱ ስቆ በድሉንም አሳቀው።
እንዲህ እንዲህ እያሉ ሲጨዋወቱ አመሹ፡፡ በድሉ ግን ለማንደፍሮ
አንዳች ምስጢር አውጥቶ አልነገረውም፡፡ በባርናባስ ምትክ ማንደፍሮ በሸዋዬ ቤት መግባቱ ለበድሉ ጉዳዩ አልነበረም። ምክንያቱ ባርናባስ ባለ ትዳር መሆንና ከአንድ ዓመት በላይ ለሆነ ጊዜ ሊቆይ መቻሉ ሌላው ነው፡፡ ከዚያም በላይ ቀድሞ ነገር
በድሉና ባርናባስ ለረጅም ጊዜ የሚተዋወቁ የአንድ ከተማ ነዋሪዎች ከመሆናቸው በቀር የተለየ ግንኙነት አልነበራቸውም፡፡ ስለዚህም ከማንደፍሮ ጋር በሸዋዬ ቤት ከመገኘቱ ለእሶም ሆነ ለእሷ የሚጎረብጣቸው ነገር እንደሌለ ያውቃል፡፡
ማንደፍሮ የበድሉና የሸዋዬ መተዋወቅ መሰረቱ ምን ሊሆን እንደሚችልም ለማወቅ ሲጓጓ ሰንብቶ አንድ ቀን ከሄደበት አገር ዶሮ፣ ሽንኩርትና ቅቤ ገዝቶ በመምጣት ለሽዋዬ እያስረከበ በነገው ዕለት ትልቅ እንግዳ ጠርቻለሁ፡፡ ከአንቺም ጋር አስተዋውቃችኋለሁ :: ሴትነትሽ ይታይበታልና አስማምሪው፡፡» አላት፡፡
ማግስቱ ቅዳሜ ነው። ወደ አሥር ሠዓት አካባቢ ሸዋዬ በሁሉም ነገር ተዘጋጅታ የማንደፍርንና የትልቁን እንግዳ መምጣት ስትጠባበቅ ማንደፍሮ ከዲላ
ይርጋለም የነበረውን የደርሶ መልስ ምድብ ስራውን አጠናቆ ከበድሉ ጋር ለማምሻ የሚበቃ ጫት ገዝተው ከሸዋዬ ቤት ከች አሉ፡፡
«እንዴ!» አለች ሸዋዬ ደስታ አይሉት ድንጋጤ አንዳች የማታውቀው ስሜት መንፈሷን ልውጥውጥ እያደረገው። ቀጥላም «አንተ ነህ እንዴ ትልቁ እንግዳ!» አለችው በድሉን ልትስመው ጠጋ እያለች።
«በአንድ ወቅት ትልቅ ነበርን፡፡ እያደር ግን…» ብሎ በድሉ ሳቅ እያለ ሸዋዪን ሲስም ማንድፍሮ ጣልቃ ገባ::
«እንተዋወቅ ነበር እንዳትለ!»
«በአንተ ቤት ገና ማስተዋወቅህ ነው!» አለችና ሸዋዬ ሁለቱም ቁጭ እንዲሉ ጋበዘቻቸው::
«ተሽውደሀል ማንዴ።» አለው በድሉ ከተነጠፈው ፍራሽ ላይ ቁጭ እያለ::
«እንዴት?» አለ ማንደፍሮ የተገረመ በመምሰል።
«ቁጫ በልና በእርጋታ ይነገርሃል።» አለው በድሉ።
«ጉድ ሳይሰሙ መስከረም አይጠባም አሉ» እያለ ማንደፍሮም ወደ ፍራሻ
አለፍ ብሎ ተቀመጠና «የሸዋ፣ በይ ከጫት በፊት የሚበላ ነገር ቶሎ በይ!» አላት።
ሸዋዬም ግርምቷን ደጋግማ እየገለጸች ምግብ የማቅረብ ስራዋን ተያያዘችው:: በድሉ ከዚያ ቤት ከቀረ ከዓመት በላይ ሆኖታል፡፡ በሽዋዬ ቤት ያየው
ለውጥ እስገረመው። የሽዋዬ ታጣፊ አልጋ ልዩ በሆነ ሞዝቦልድ አልጋ ተተክታለች፣ ለብቻ ቢተኙበት
'የሰው ያለህ' የሚያሰኝ፡፡ ከፊትለፊቱ ባለ መስታወት
ብፌ ግድግዳ ጥግ ይዞ ተሰይሟል። የጓዳው በር እንኳ መጋረጃው ዓይን ይስባል።
ቤቱ በሮዝ ቀለም ተቀብቶ ፍክት ብሏል። ሁሉመሰ ነገር ደስ ይላል። ይህን ሁሉ ሲያጤን ቆይቶ የሸዋዬን ጓዳ ውስጥ መሆን አጋጣሚ በመጠቀም ወደ ማንደፍሮ ጆሮ ጠጋ በማለት በሹክሹታ አነጋገር «ምን መሰረት ጥያለሁ ትላለህ ዋልታውንም
አቁምሃል እንጂ» አለና ለራሱ እየሳቀ ማንደፍሮንም አሳቀው።
ሽዋዬ እንጀራና ወጡን ለበድሉና ለማንደፍሮ አቅርባ እየጋበዘች እሷ ግን የቡና ማፍላቱን ስራ ቀጠለች፡፡ ግን ከእነሱ ይበልጥ እሷ ነበረች የምትበላው ሁለቱም እየተፈራረቁ በሚያጎርሷት ጉርሻ ጉንጯ እየሞላ ስራ ያለማቋረጧ ደግሞ ለቡናው
👍14
ቶሎ መድረስና ለጫት ቅሞሹ መጀመር አስተዋፅዎ አደረገ ።
«ማንዴ» ሲል ጠራው በድሉ ጫቱን አጎንብሶ እየቀነጣጠበ
«ወይ»
«አንተ እዚህ ቤት አባወራ ከመሆንህ በፊት እኔ ደግሞ አማች ነበርኩ።
«ማንን አግብተህ?» አለ ማንደፍሮ በድሉን ሸዋዬንም ተራ በተራ
እየተመለከተ፡፡ ከዚህ በኋላ ለሚወራው ሁሉ ማንደፍሮ አዲስ ስለሆነ ቀልቡ ይጓጓ ጀመር።
«ቀሪውን ሸዋዬ ትንገርህ»
«ቅልጥፍና ጎድሎህ ያጣኸውን ዕድል አሁን ለምን ታነሳሳለህ?» አለች ሸዋዬ ፈገግ ብላ በድሉንም ማንደፍሮንሃ" እያየች።
«እኔ በድሉ!?»
«እኔ ሽዋዬ ነኛ»
«አሪፍ ጨዋታ ልሰማ ነው፡፡» አለ ማንደፍሮ ሁለቱንም እያየ።
«ምን ዋጋ አለው! በወሬ ቀረ፡፡» ብሎ በድሉ በቁጭት ዓይነት ራሱን
ወዝወዝ ሲያደርግ ማንደፍሮ ቀጠለ፡፡ እንዴት? ለምን?
«በቃ! አቃተው፣ ቀረ፡፡» አለች ሽዋዬ።
«ልጃገረድ ነበረች?» ሲል ማንደፍሮ ጠየቀ በተለይ ሸዋዬን እየተመለከተ።
«ቀድሞ ማን ወንድ ሆኖ እዚያ ቦታ ደረሰና!» አለችና ሽዋዬ ኪ ኪ ኪ ኪ... ብላ ሳቀች።
«ወንድሜ ጉድ ሆነሃላ!» በማለት ማንደፍሮ በድሉን ቀለደበት
«ዝም በላት ትቀልድ፣ ቀስ እያልክ ምስጢሩን ታገኘው የለ» አለና በድሉ የተቀነጣጠበውን ጫት አፉ አደረገ።
«ልጅቱ አሁን የት ናት?» ሲል ጠየቀ ማንደፍሮ፡፡
«እህቷ ናትና አሷ ናት የምታውቀው::
«እንዴ!» ብሎ እንደ መደነቅ አለና ማንደፍሮ «ለዚያውም እህትሽ?» ሲል፣ በተለይ ሸዋዬን ጠየቃት።
«ባለ ጉዳይ ይፈልጋት እንጂ እኔ ምን አገባኝ፡፡»
« አቦ ልቤን አታንጠልጥሉት!» አለና ማንደፍሮ እንደ መናደድ ብሎ
«ትነግሩኝ እንደሆነ ንገሩኝ!» ብሎ ቀነጣጥቦ እጁ ላይ ያጠራቀመውን ጫት ቃመው።
«ሩቅ አገር ነው ያለችው፡፡»አለችው ሽዋዬ::
«መኪና አይገባውም?»
«ሄደህ ልታመጣለት? ኪ-ኪ-ኪ-ኪ ..»
ምን ችግር አለ? የምነዳው የአባቱን መኪና»
«ከመቼ ጀምሮ?» አለች ሸዋዬ በቁም ነገር። መኪና መቀየሩን አልሰማችም ማንደፍሮ ያልነገራት በድሉ ባሳሰበው መሰረት ነው። ያም የሆነው የዛሬውን የሸዋዬን ግርምት ለመፍጠር በማሰብ ነበር።
«ለነገሩ እንኳ ከሳምንት በላይ አይሆንም።» አላት ማንደፍሮ በመጠኑም ቢሆን እንደ እፍረት እየተሰማው።
«እንዴ!» አለች ሸዋዬ እውነትም ነገሩ ዱብ እዳ ሆኖባት። ሁለቱ ሰዎች እሷ የማታውቀው ምስጢር ይኖራቸው እንደሆነ ብላም ተጠራጠረችና ተራ በተራ ታያቸው ጀመር። ሁኔታዋ የገባቸው
በድሉና ማንደፍሮ የተገናኙበትን አጋጣሚ ዝርዝር አድርገው
ሲያስረዷት ወደ ማመኑ አዘነበለች። የተጀመረው ጨዋታ ቀጠለ።
«እውነት ግን ልጅቷ መምጣት አትችልም?» ሲል ማንደፍሮ ጠየቃቸው ሁለቱንም ተራበተራ እየተመለከታቸው።
እንዴት ነው የሸዋ ይኸ ነገር አላት ማንደፍሮም ሸዋዬን እየተመለከተ፡፡
«ይሆን አይመስለኝም" አለች ሸዋዬ፡፡ ግን ደግሞ ድንገት ፍዝዝ ትክዝ በማለት ከሃሳብ ውስጥ የገባች መሰለች። ሸዋዬ እውነትም ጭልጥ ብላ ከሀሳብ ውስጥ ገባች:: እንኳን በውኗ በህልሟ እንኳ ታይቷት የማያውቅ አዲስ ሀሳብ በአዕምሮዋ ተፈጠረ። እውነት ሔዋን በዚህ አጋጣሚ ወደ ዲላ ብትመጣስ የሚል
ሀሳብ በውስጧ ተመላለስ። መንገዱ እንደሆነ ክፍት ሆኗል፣ አስቻለው ከዘመቻ አልተመለሰም፡፡ ወደፊት ቢመጣ እንኳ ሁኔታዎች ሁሉ መሠረታቸው ከተለወጡ ምን ሊፈጠር ይችላል። እንዲያውም ሔዋንን ከበድሉ ጋር የማቆራኘት ምኞቷ ተሳክቶ የሔዋን ህይወት የተሻለ ቢሆን 'ይኸው የኔም አላማ ይኸ ነበር' እያለች ለሞፈከርና በተለይ ከእናቷ ጋር የሻከረባት ግኑኝነት ሊስተካከል እንደሚችል ይታያት ጀመር።
ምናልባት የሔዋንና የበድሉ ግንኙነት እሷም ከማንደፍሮ ጋር ያላትን ግንኙነት መሰረቱን እያጣበቀው ሊሄድ ይችላል፡፡ ሸዋዬ ደስ ደስ የሚል ስሜት ይሰማት ጀመር፡፡ ድንገት እፍን የሚያደርጋት ግን ሔዋንን የምታገኝበት መንገድ! በእርግጥ
ሔዋን እሷን ተማምና ወደ ዲላ ትመጣ ይሆን? እናቷስ እሷን አምነው ሔዋን ከክብረ መንግስት ትመጣ ዘንድ ይፈቅዱ ይሆን? አሳሳቢና አስጨናቂ ጉዳይ!
«አንድ ነገር በይ እንጂ የሽዋ ምነው ዝም አልሽ?» ሲል ማንደፍር ከሃሳቧ ቀሰቀሳት።
«እስቲ እየዋልን እያደርን»....
💫ይቀጥላል💫
«ማንዴ» ሲል ጠራው በድሉ ጫቱን አጎንብሶ እየቀነጣጠበ
«ወይ»
«አንተ እዚህ ቤት አባወራ ከመሆንህ በፊት እኔ ደግሞ አማች ነበርኩ።
«ማንን አግብተህ?» አለ ማንደፍሮ በድሉን ሸዋዬንም ተራ በተራ
እየተመለከተ፡፡ ከዚህ በኋላ ለሚወራው ሁሉ ማንደፍሮ አዲስ ስለሆነ ቀልቡ ይጓጓ ጀመር።
«ቀሪውን ሸዋዬ ትንገርህ»
«ቅልጥፍና ጎድሎህ ያጣኸውን ዕድል አሁን ለምን ታነሳሳለህ?» አለች ሸዋዬ ፈገግ ብላ በድሉንም ማንደፍሮንሃ" እያየች።
«እኔ በድሉ!?»
«እኔ ሽዋዬ ነኛ»
«አሪፍ ጨዋታ ልሰማ ነው፡፡» አለ ማንደፍሮ ሁለቱንም እያየ።
«ምን ዋጋ አለው! በወሬ ቀረ፡፡» ብሎ በድሉ በቁጭት ዓይነት ራሱን
ወዝወዝ ሲያደርግ ማንደፍሮ ቀጠለ፡፡ እንዴት? ለምን?
«በቃ! አቃተው፣ ቀረ፡፡» አለች ሽዋዬ።
«ልጃገረድ ነበረች?» ሲል ማንደፍሮ ጠየቀ በተለይ ሸዋዬን እየተመለከተ።
«ቀድሞ ማን ወንድ ሆኖ እዚያ ቦታ ደረሰና!» አለችና ሽዋዬ ኪ ኪ ኪ ኪ... ብላ ሳቀች።
«ወንድሜ ጉድ ሆነሃላ!» በማለት ማንደፍሮ በድሉን ቀለደበት
«ዝም በላት ትቀልድ፣ ቀስ እያልክ ምስጢሩን ታገኘው የለ» አለና በድሉ የተቀነጣጠበውን ጫት አፉ አደረገ።
«ልጅቱ አሁን የት ናት?» ሲል ጠየቀ ማንደፍሮ፡፡
«እህቷ ናትና አሷ ናት የምታውቀው::
«እንዴ!» ብሎ እንደ መደነቅ አለና ማንደፍሮ «ለዚያውም እህትሽ?» ሲል፣ በተለይ ሸዋዬን ጠየቃት።
«ባለ ጉዳይ ይፈልጋት እንጂ እኔ ምን አገባኝ፡፡»
« አቦ ልቤን አታንጠልጥሉት!» አለና ማንደፍሮ እንደ መናደድ ብሎ
«ትነግሩኝ እንደሆነ ንገሩኝ!» ብሎ ቀነጣጥቦ እጁ ላይ ያጠራቀመውን ጫት ቃመው።
«ሩቅ አገር ነው ያለችው፡፡»አለችው ሽዋዬ::
«መኪና አይገባውም?»
«ሄደህ ልታመጣለት? ኪ-ኪ-ኪ-ኪ ..»
ምን ችግር አለ? የምነዳው የአባቱን መኪና»
«ከመቼ ጀምሮ?» አለች ሸዋዬ በቁም ነገር። መኪና መቀየሩን አልሰማችም ማንደፍሮ ያልነገራት በድሉ ባሳሰበው መሰረት ነው። ያም የሆነው የዛሬውን የሸዋዬን ግርምት ለመፍጠር በማሰብ ነበር።
«ለነገሩ እንኳ ከሳምንት በላይ አይሆንም።» አላት ማንደፍሮ በመጠኑም ቢሆን እንደ እፍረት እየተሰማው።
«እንዴ!» አለች ሸዋዬ እውነትም ነገሩ ዱብ እዳ ሆኖባት። ሁለቱ ሰዎች እሷ የማታውቀው ምስጢር ይኖራቸው እንደሆነ ብላም ተጠራጠረችና ተራ በተራ ታያቸው ጀመር። ሁኔታዋ የገባቸው
በድሉና ማንደፍሮ የተገናኙበትን አጋጣሚ ዝርዝር አድርገው
ሲያስረዷት ወደ ማመኑ አዘነበለች። የተጀመረው ጨዋታ ቀጠለ።
«እውነት ግን ልጅቷ መምጣት አትችልም?» ሲል ማንደፍሮ ጠየቃቸው ሁለቱንም ተራበተራ እየተመለከታቸው።
እንዴት ነው የሸዋ ይኸ ነገር አላት ማንደፍሮም ሸዋዬን እየተመለከተ፡፡
«ይሆን አይመስለኝም" አለች ሸዋዬ፡፡ ግን ደግሞ ድንገት ፍዝዝ ትክዝ በማለት ከሃሳብ ውስጥ የገባች መሰለች። ሸዋዬ እውነትም ጭልጥ ብላ ከሀሳብ ውስጥ ገባች:: እንኳን በውኗ በህልሟ እንኳ ታይቷት የማያውቅ አዲስ ሀሳብ በአዕምሮዋ ተፈጠረ። እውነት ሔዋን በዚህ አጋጣሚ ወደ ዲላ ብትመጣስ የሚል
ሀሳብ በውስጧ ተመላለስ። መንገዱ እንደሆነ ክፍት ሆኗል፣ አስቻለው ከዘመቻ አልተመለሰም፡፡ ወደፊት ቢመጣ እንኳ ሁኔታዎች ሁሉ መሠረታቸው ከተለወጡ ምን ሊፈጠር ይችላል። እንዲያውም ሔዋንን ከበድሉ ጋር የማቆራኘት ምኞቷ ተሳክቶ የሔዋን ህይወት የተሻለ ቢሆን 'ይኸው የኔም አላማ ይኸ ነበር' እያለች ለሞፈከርና በተለይ ከእናቷ ጋር የሻከረባት ግኑኝነት ሊስተካከል እንደሚችል ይታያት ጀመር።
ምናልባት የሔዋንና የበድሉ ግንኙነት እሷም ከማንደፍሮ ጋር ያላትን ግንኙነት መሰረቱን እያጣበቀው ሊሄድ ይችላል፡፡ ሸዋዬ ደስ ደስ የሚል ስሜት ይሰማት ጀመር፡፡ ድንገት እፍን የሚያደርጋት ግን ሔዋንን የምታገኝበት መንገድ! በእርግጥ
ሔዋን እሷን ተማምና ወደ ዲላ ትመጣ ይሆን? እናቷስ እሷን አምነው ሔዋን ከክብረ መንግስት ትመጣ ዘንድ ይፈቅዱ ይሆን? አሳሳቢና አስጨናቂ ጉዳይ!
«አንድ ነገር በይ እንጂ የሽዋ ምነው ዝም አልሽ?» ሲል ማንደፍር ከሃሳቧ ቀሰቀሳት።
«እስቲ እየዋልን እያደርን»....
💫ይቀጥላል💫
👍10❤1
#የራስ_ጥናት
አንባቢ አዋቂ ነው
ማንበብ ሰው ያደርጋል
ሲባል ሰማሁና
መፅሐፋን ብገልጠው
የሰው መሰረቱ የኑሮ ብልሃቱ
ራስን ማወቅ ነው ሲለኝ እያብራራ
መፅሐፉን ዘግቼ ሙከራ ጀመርኩኝ
ራሴን ላጠና.....
ራሴን ሳነበው...
አንቀፅም ምዕራፍም መግቢያም መደምደሚያም
ማውጫ ገፅ የሌለው
የምኞት ጋጋታ
የኑሮ ሁካታ ትልቅ ጎተራ ነው
ከዚህ ሁሉ መሃል
ለ ‹ማን ነኝ?ጥያቄ
ለራሴ ከራሴ መልሱን ስላጣሁት
የከፈትኩትን ራስ መልሼ ዘጋሁት።
🔘ልዑል ሀይሌ🔘
አንባቢ አዋቂ ነው
ማንበብ ሰው ያደርጋል
ሲባል ሰማሁና
መፅሐፋን ብገልጠው
የሰው መሰረቱ የኑሮ ብልሃቱ
ራስን ማወቅ ነው ሲለኝ እያብራራ
መፅሐፉን ዘግቼ ሙከራ ጀመርኩኝ
ራሴን ላጠና.....
ራሴን ሳነበው...
አንቀፅም ምዕራፍም መግቢያም መደምደሚያም
ማውጫ ገፅ የሌለው
የምኞት ጋጋታ
የኑሮ ሁካታ ትልቅ ጎተራ ነው
ከዚህ ሁሉ መሃል
ለ ‹ማን ነኝ?ጥያቄ
ለራሴ ከራሴ መልሱን ስላጣሁት
የከፈትኩትን ራስ መልሼ ዘጋሁት።
🔘ልዑል ሀይሌ🔘
👍17❤7👎1🔥1
#ምንትዋብ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንም እንኳን ልጇ ደሕና መሆኑንና ትምህርትና ዋናም እየተማረ እንደሆነ፣ ከፍ ሲል ደግሞ ቀስት ውርወራ፣ ጉግስና አደን እንደሚማር ብትሰማም፣ ጭንቀቷ እምብዛም ሊቀንስላት አልቻለም። ሳታስበው ግን ሁኔታዎች ተቀየሩ። ለንጉሠ ነገሥቱ ቅርብ የሆነው ዐቃቤ ሰዐቱ ዲዮስቆሮስ ንጉሠ ነገሥቱን፣ “ኢያሱ መጥቶ የቤተመንግሥት ወግ፣
አስተዳደርና ትምርት በአግባቡ ይማር፤ ባባትዎ አጥንት ይዤዎታለሁ”እያለ አላስቆም አላስቀምጥ አላቸው።
ምንትዋብ አጋዥ ያገኘች መሰላት
አንድ ቀን ያልታሰበ ነገር ተፈጠረ። የስድስት ዓመቱ ኢያሱ ሲጫወት ድንገት በቀስት የሰው ጊደር ወጋ። የጊደሩን ባለቤት ፈርቶ ከዐይን ተሰወረ። ሲፈለግ በመጥፋቱ ክርስትና አባቱ፣ የእህቱ ባል
ደጃዝማች ባስልዮስና የአካባቢው ነዋሪ በጭንቀት አካባቢውን አሰሱ::ሰፈርተኛው ሁሉ በደቦ ተከፋፍሎ ቀየውን፣ ወንዙንና ጫካውን ፈተሽ::ኢያሱ የውሃ ሽታ ሆነ። ሰዉ ተደናገጠ፣ የሚያደርገው ጠፋው። ብሎም
ኡኡታ፣ ለቅሶና ጩኸት በረከተ። ለንጉሠ ነገሥቱና ለምንትዋብ
እንዴት እንደሚነገራቸው ተመከረ።
ኢያሱ ከተደበቀበት ሲወጣ ዕልልታና ደስታ ጩኸትንና ለቅሶን
ተኩ። ማንነቱ ተደብቆ የኖረው ልጅ በዚህ አጋጣሚ ማንነቱ ታወቀ።
ደጃዝማች ባስልዮስ ግን የኢያሱ ማንነት መታወቁ አደገኛና አሳሳቢ
መሆኑን ተረድቶ በሐሳብ ማሰነ። አፄ በካፋ ጉዳዩን እንዲሰሙ አደረገ።ኢያሱም በፍጥነት ጐንደር እንዲመለስ ተደረገ። ምንትዋብ፣ እናቷና አያቷ የደስታና የእፎይታ እንባ አነቡ።
ምንትዋብ ሳትውል ሳታድር፣ ኢያሱ በተመረጡ አስተማሪዎች
ትምህርት እንዲማር አደረገች። የመንፈስ፣ የግብረገብ፣ የአካል ግንባታና የቤተመንግሥት ወግ ትምህርትም ላይ አተኮረች።
አፄ በካፋ ጠላቶቼ ይገድሉብኛል ብለው ስጋት ቢገባቸውም፣ ዝምታን ፈቀዱ። በሌላ በኩል ግን ከእሷ፣ ከእመቤት እንኰዬ፣ ከእመቤት ዮልያናና ከግራዝማች ኒቆላዎስ ጋር ብዙ ጊዜ ቆይታ መያዝ አዘወተሩ።
በተለይ ምንትዋብን፣ “አንቺ ብልህና አስተዋይ ስለ ሆንሽ እኔ ሳልኖር ኸልዤ ጋር ሁነሽ አገሬን ባግባቡ እንድትመሪ፣ እንድታስተዳድሪ።
የባሕር ማዶ አረመኔዎች አገሬ ገብተው እንዳይበጠብጡ፤ ሕዝቤንም በሃይማኖት ሆነ በሌላ እንዳይበክሉ ዐደራ” ይሏታል።
በነገሡ በዘጠነኛው ዓመት መጀመሪያ ላይ ጥቅምት ወር ውስጥ ግን፣
“ወዳጅ ዘመዴን እለያለሁ” በሚል ታመምኩ ብለው ሲደበቁ ምንትዋብ
ምሥጢር ጠበቀች። ወዲያው፣ “ንጉሡ ሊሞቱ ነው”፣ “ንጉሡ ሙተዋል” የሚል ወሬ ጐንደርን አወዛገባት። የጐንደር ከንቲባ ብላቴን ጌታ ኩቾ ከወህኒ አምባ ንጋሢ አመጣለሁ' ብሎ ሠራዊት አዘጋጀ። ወህኒ አምባዎች በበኩላቸው ወሬውን ሲሰሙ እኔ ልንገሥ፣ አንተ ንገሥ፣ የለም እሱ ይንገሥ ተባባሉ፤ ተመራረጡ፤ ተፎካከሩ።
ጐንደር እንደ ልማዷ ልትታመስ ሆነ።
በካፋ ይህን ሲሰሙ አለመታመማቸውን ለማሳየት ሐሙስ ቀን ደብረብርሃን ሥላሤ ሲሄዱ፣ መኳንንቱ በርቀት ከጋሻ ጃግሬዎች ኋላ በፈረስ ተከተሏቸው። ሕዝቡም ከየቤቱ እንደ ጎርፍ ፍንቅል ብሎ
ወጣ፡፡
በካፋ፣ ሕዝቡን፣ “ታዩኛላችሁና ወደየቤታችሁ ግቡ” ብለው አሰናበቱ።ሊቃውንት ንጉሠ ነገሥቱን በሕይወት በማየታቸው መሬት ሳሙ፤ካህናት ዘመሩ፤ ሕዝቡ ተደሰተ። ከረብሻ ዳነ። በካፋ ግን ብዙ ታዘቡ።
ወዳጅ መሳይ ሁሉ ከበስተጀርባቸው ምን እንደሚያስብ ተረዱ።
መኳንንቱን ወርቅ ሰቀላ ጠርተው፣ በአፈ ንጉሥ በኩል፣ “ምነው
ባካችሁ እንዳው ጥቂት ቀን ታምሜ ብተኛ ሽብር ማስነሳታችሁ? ስለምን ከተማዬን አስደነገጣችኋት? ሞተ ብላችሁ እንደዝኸ መሆናችሁ ተገቢ ነውን?” ሲሉ ጠየቋቸው። እንደማይተኙላቸውም ተረዱ። ሆኖም፣“እነዝኸ በልባቸው ክፋት የለም” ብለው ይቅርታ አደረጉላቸው።መሣሪያ ያነሳው ኩቾ ግን ከነተከታዮቹ ተይዞ ጊዜያዊ እስር ቤት ገብቶ ለፍርድ እንዲቀርብ ተወስኖበት ፍርድ ሸንጎ ቀረበ።
የሃገር ክህደት ወይም ሌላ ከፍተኛ ወንጀል ካልሆነ በስተቀር የዙፋን
ችሎት የማይዙት ንጉሠ ነገሥት፡ ጃን ተከል ተገኝተው ከምንትዋብ ጋር እንደወትሯቸው ቀይ ድባብ ተይዞላቸው፣ ከፍ ያለ ቦታ ላይ ተቀመጡ።መሣፍንቱ፣ መኳንንቱና ሊቃውንቱ እንደየደረጃቸው ተሰየሙ። ፍትሐ ነገሥት ተርጓሚዎቹ፣ ፍርድ ሰጭዎቹና አዛዦቹ፣ ግራ ቀኝ ተችዎቹ
ሁሉ ተገኝተዋል። ዐራቱ ሊቃውንት ፍትሐ ነገሥት ይዘው ቦታቸው
ላይ ተቀመጡ። አቡኑ፣ ዐቃቤ ሰዐቱና መኳንንቱ የተለመደ ቦታቸው ላይ ሆኑ።
ኩቾና ተከታዮቹ እግራቸው በእግረ ሙቅ ታስሮ፣ ጋሻ ጃግሬዎች
ግራና ቀኝ እየጠበቋቸው በንጉሠ ነገሥቱ ትይዩ ቆሙ።ከአዛዦቹ አንደኛው፣ “ጠበቃ ኸፈለግህ ይፈቀድልኻል” አለው፣
ኩቾን።
“አያሻኝም።”
“እንግዲያማ ተጠየቅ።”
“ልጠየቅ!”
“አንድ ስጠይቅህ አንድ፣ ሁለት ስሰጥህ ሁለት መልስልኝ። ኸዝኽ
እንዳትዛነፍ በቅሎ ያግድህ። ጃንሆይ ትንሽ አሟቸው ሰንብተው
እንደነበር አልሰማህም?”
“ሰምቻለሁ።”
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ጃንሆይን አደባባይ ባታያቸው ሊሞቱ ነው ብለህ አላወራህም?”
“አላወራሁም።”
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ያለ ጃንሆይ ፈቃድ ሠራዊትህን ማንቀሳቀስ እንደማትችል
ታውቃለህ አታውቅም?”
“አውቃለሁ ።"
“ተጠየቅ!"
“ልጠየቅ!”
“ዛዲያ ስለምን ሠራዊትህን አንቀሳቅሰህ ለአመጥ ተነሳህ?”
“ለአመጥ አልተነሳሁም።”
“ምስክር ይጠራብህ?”
“ሠራዊት...”
"አንድ ስጠይቅህ አንድ፣ ሁለት ስሰጥህ ሁለት መልስልኝ ያልኩህን አጣርሰኻል። ለበቅሎ ዋስ ጥራ።”
“አላጣረስሁም።”
“አጣርሰኻል። ምስክር ይጠራብኝ ወይንም አይጠራብኝ ነበር
መልሱ።”
“ኸጥያቄህ አልወጣሁም። እማኞች ይጠሩልኝ” እያለ ወደ ሰዉ ተመለከተ ኩቾ።
“አጣርሷል! አጣርሷል! በቅሎዋን ይክፈል!” አለ፣ ሰዉ።
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ለአመጥ መሣሪያ አላነሳህም?”
“ራስ ተስፋ ኢየሱስና ቢትወደድ ስኩት ጃንሆይ ያስሩኻል ቢሉኝ
መሣሪያ አነሳሁ።”
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ምንም ሳታደርግ ጃንሆይ ስለምን ያስሩኻል? ሞተዋል ብለህ
ስላስወራህና ኸወህኒ ነጋሢ ልታመጣ ስለፈለግህ ነው እነራስ ተስፋ ኢየሱስ ያስሩኻል ያሉህ።”
ኩቾ ወደ እፄ በካፋ ተመለከተ። ሁለት እጆቹን ዘርግቶ፣ “ጃንሆይ
ይማሩኝ” ብሎ አጎነበሰ።
“ምትጠይቀው ጥያቄ አለ?” ሲል ጠየቀው አንደኛው አዛዥ ።
“የለኝም። ምሕረት ያርጉልኝ ጃንሆይ!” አለ፣ ኩቾ፣ አጎንብሶ።
ከአዛዦቹ አንደኛው ጋቢውን አስተካከለና ወደ ንጉሠ ነገሥቱ
ተመለከተ፣ “ጃንሆይ ኩቾ የቀረበበት ክስ ክህደት ነው። ክህደት ደሞ በሞት ያስቀጣል” አለ፣ ፍትሐ ነገሥቱን እያገላበጠ። “ፍታ ነገሥቱ ሚለው በንጉሥ ላይ ያመጠና ያሳመጠ በሞት ይቀጣ ነው።”
ይህን ዓይነቱ የሞት ብይን ይገባዋል አይገባውም፤ ወይንም ደግሞ ሌላ ቅጣት ይቀጣ ብለው ለመወሰን መኳንንት እንደየማዕረጋቸው እየቆሙ ከዝቅተኛው ጀምሮ እስከ ከፍተኛው ድረስ አስተያየት ሰጡ።
“ክህደት ነውና ሞት ይገባዋል!” አሉ፣ አንደኛው መኰንን።
“ግዞት ይላክ!” አሉ፣ ሌላው።
“በግርፋት ይቀየርለት!” ብለው ተቀመጡ፣ አንደኛው
“ጃንሆይ መሐሪ ናቸውና ምህረት ይደረግለትና ሹመቱን ይገፈፍ”
አሉ፣ ሌላኛው።
እንደዚህ እያለ ሁሉም ተናግረው ከጨረሱ በኋላ፣ የማሳረጊያው
ንግግር የንጉሠ ነገሥቱ በመሆኑ፣ አፈ ንጉሡ አጎንብሶ ጆሮውን
ሲሰጣቸው ሁሉም ለመስማት ጆሯቸውን ሲያቀኑ ኩቾና ተከታዮቹ
ትንፋሻቸውን ውጠው ተጠባበቁ። ይህን ሁሉ በአንክሮ የምትመለከተው ምንትዋብም ተጠባበቀች።
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ
....ምንም እንኳን ልጇ ደሕና መሆኑንና ትምህርትና ዋናም እየተማረ እንደሆነ፣ ከፍ ሲል ደግሞ ቀስት ውርወራ፣ ጉግስና አደን እንደሚማር ብትሰማም፣ ጭንቀቷ እምብዛም ሊቀንስላት አልቻለም። ሳታስበው ግን ሁኔታዎች ተቀየሩ። ለንጉሠ ነገሥቱ ቅርብ የሆነው ዐቃቤ ሰዐቱ ዲዮስቆሮስ ንጉሠ ነገሥቱን፣ “ኢያሱ መጥቶ የቤተመንግሥት ወግ፣
አስተዳደርና ትምርት በአግባቡ ይማር፤ ባባትዎ አጥንት ይዤዎታለሁ”እያለ አላስቆም አላስቀምጥ አላቸው።
ምንትዋብ አጋዥ ያገኘች መሰላት
አንድ ቀን ያልታሰበ ነገር ተፈጠረ። የስድስት ዓመቱ ኢያሱ ሲጫወት ድንገት በቀስት የሰው ጊደር ወጋ። የጊደሩን ባለቤት ፈርቶ ከዐይን ተሰወረ። ሲፈለግ በመጥፋቱ ክርስትና አባቱ፣ የእህቱ ባል
ደጃዝማች ባስልዮስና የአካባቢው ነዋሪ በጭንቀት አካባቢውን አሰሱ::ሰፈርተኛው ሁሉ በደቦ ተከፋፍሎ ቀየውን፣ ወንዙንና ጫካውን ፈተሽ::ኢያሱ የውሃ ሽታ ሆነ። ሰዉ ተደናገጠ፣ የሚያደርገው ጠፋው። ብሎም
ኡኡታ፣ ለቅሶና ጩኸት በረከተ። ለንጉሠ ነገሥቱና ለምንትዋብ
እንዴት እንደሚነገራቸው ተመከረ።
ኢያሱ ከተደበቀበት ሲወጣ ዕልልታና ደስታ ጩኸትንና ለቅሶን
ተኩ። ማንነቱ ተደብቆ የኖረው ልጅ በዚህ አጋጣሚ ማንነቱ ታወቀ።
ደጃዝማች ባስልዮስ ግን የኢያሱ ማንነት መታወቁ አደገኛና አሳሳቢ
መሆኑን ተረድቶ በሐሳብ ማሰነ። አፄ በካፋ ጉዳዩን እንዲሰሙ አደረገ።ኢያሱም በፍጥነት ጐንደር እንዲመለስ ተደረገ። ምንትዋብ፣ እናቷና አያቷ የደስታና የእፎይታ እንባ አነቡ።
ምንትዋብ ሳትውል ሳታድር፣ ኢያሱ በተመረጡ አስተማሪዎች
ትምህርት እንዲማር አደረገች። የመንፈስ፣ የግብረገብ፣ የአካል ግንባታና የቤተመንግሥት ወግ ትምህርትም ላይ አተኮረች።
አፄ በካፋ ጠላቶቼ ይገድሉብኛል ብለው ስጋት ቢገባቸውም፣ ዝምታን ፈቀዱ። በሌላ በኩል ግን ከእሷ፣ ከእመቤት እንኰዬ፣ ከእመቤት ዮልያናና ከግራዝማች ኒቆላዎስ ጋር ብዙ ጊዜ ቆይታ መያዝ አዘወተሩ።
በተለይ ምንትዋብን፣ “አንቺ ብልህና አስተዋይ ስለ ሆንሽ እኔ ሳልኖር ኸልዤ ጋር ሁነሽ አገሬን ባግባቡ እንድትመሪ፣ እንድታስተዳድሪ።
የባሕር ማዶ አረመኔዎች አገሬ ገብተው እንዳይበጠብጡ፤ ሕዝቤንም በሃይማኖት ሆነ በሌላ እንዳይበክሉ ዐደራ” ይሏታል።
በነገሡ በዘጠነኛው ዓመት መጀመሪያ ላይ ጥቅምት ወር ውስጥ ግን፣
“ወዳጅ ዘመዴን እለያለሁ” በሚል ታመምኩ ብለው ሲደበቁ ምንትዋብ
ምሥጢር ጠበቀች። ወዲያው፣ “ንጉሡ ሊሞቱ ነው”፣ “ንጉሡ ሙተዋል” የሚል ወሬ ጐንደርን አወዛገባት። የጐንደር ከንቲባ ብላቴን ጌታ ኩቾ ከወህኒ አምባ ንጋሢ አመጣለሁ' ብሎ ሠራዊት አዘጋጀ። ወህኒ አምባዎች በበኩላቸው ወሬውን ሲሰሙ እኔ ልንገሥ፣ አንተ ንገሥ፣ የለም እሱ ይንገሥ ተባባሉ፤ ተመራረጡ፤ ተፎካከሩ።
ጐንደር እንደ ልማዷ ልትታመስ ሆነ።
በካፋ ይህን ሲሰሙ አለመታመማቸውን ለማሳየት ሐሙስ ቀን ደብረብርሃን ሥላሤ ሲሄዱ፣ መኳንንቱ በርቀት ከጋሻ ጃግሬዎች ኋላ በፈረስ ተከተሏቸው። ሕዝቡም ከየቤቱ እንደ ጎርፍ ፍንቅል ብሎ
ወጣ፡፡
በካፋ፣ ሕዝቡን፣ “ታዩኛላችሁና ወደየቤታችሁ ግቡ” ብለው አሰናበቱ።ሊቃውንት ንጉሠ ነገሥቱን በሕይወት በማየታቸው መሬት ሳሙ፤ካህናት ዘመሩ፤ ሕዝቡ ተደሰተ። ከረብሻ ዳነ። በካፋ ግን ብዙ ታዘቡ።
ወዳጅ መሳይ ሁሉ ከበስተጀርባቸው ምን እንደሚያስብ ተረዱ።
መኳንንቱን ወርቅ ሰቀላ ጠርተው፣ በአፈ ንጉሥ በኩል፣ “ምነው
ባካችሁ እንዳው ጥቂት ቀን ታምሜ ብተኛ ሽብር ማስነሳታችሁ? ስለምን ከተማዬን አስደነገጣችኋት? ሞተ ብላችሁ እንደዝኸ መሆናችሁ ተገቢ ነውን?” ሲሉ ጠየቋቸው። እንደማይተኙላቸውም ተረዱ። ሆኖም፣“እነዝኸ በልባቸው ክፋት የለም” ብለው ይቅርታ አደረጉላቸው።መሣሪያ ያነሳው ኩቾ ግን ከነተከታዮቹ ተይዞ ጊዜያዊ እስር ቤት ገብቶ ለፍርድ እንዲቀርብ ተወስኖበት ፍርድ ሸንጎ ቀረበ።
የሃገር ክህደት ወይም ሌላ ከፍተኛ ወንጀል ካልሆነ በስተቀር የዙፋን
ችሎት የማይዙት ንጉሠ ነገሥት፡ ጃን ተከል ተገኝተው ከምንትዋብ ጋር እንደወትሯቸው ቀይ ድባብ ተይዞላቸው፣ ከፍ ያለ ቦታ ላይ ተቀመጡ።መሣፍንቱ፣ መኳንንቱና ሊቃውንቱ እንደየደረጃቸው ተሰየሙ። ፍትሐ ነገሥት ተርጓሚዎቹ፣ ፍርድ ሰጭዎቹና አዛዦቹ፣ ግራ ቀኝ ተችዎቹ
ሁሉ ተገኝተዋል። ዐራቱ ሊቃውንት ፍትሐ ነገሥት ይዘው ቦታቸው
ላይ ተቀመጡ። አቡኑ፣ ዐቃቤ ሰዐቱና መኳንንቱ የተለመደ ቦታቸው ላይ ሆኑ።
ኩቾና ተከታዮቹ እግራቸው በእግረ ሙቅ ታስሮ፣ ጋሻ ጃግሬዎች
ግራና ቀኝ እየጠበቋቸው በንጉሠ ነገሥቱ ትይዩ ቆሙ።ከአዛዦቹ አንደኛው፣ “ጠበቃ ኸፈለግህ ይፈቀድልኻል” አለው፣
ኩቾን።
“አያሻኝም።”
“እንግዲያማ ተጠየቅ።”
“ልጠየቅ!”
“አንድ ስጠይቅህ አንድ፣ ሁለት ስሰጥህ ሁለት መልስልኝ። ኸዝኽ
እንዳትዛነፍ በቅሎ ያግድህ። ጃንሆይ ትንሽ አሟቸው ሰንብተው
እንደነበር አልሰማህም?”
“ሰምቻለሁ።”
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ጃንሆይን አደባባይ ባታያቸው ሊሞቱ ነው ብለህ አላወራህም?”
“አላወራሁም።”
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ያለ ጃንሆይ ፈቃድ ሠራዊትህን ማንቀሳቀስ እንደማትችል
ታውቃለህ አታውቅም?”
“አውቃለሁ ።"
“ተጠየቅ!"
“ልጠየቅ!”
“ዛዲያ ስለምን ሠራዊትህን አንቀሳቅሰህ ለአመጥ ተነሳህ?”
“ለአመጥ አልተነሳሁም።”
“ምስክር ይጠራብህ?”
“ሠራዊት...”
"አንድ ስጠይቅህ አንድ፣ ሁለት ስሰጥህ ሁለት መልስልኝ ያልኩህን አጣርሰኻል። ለበቅሎ ዋስ ጥራ።”
“አላጣረስሁም።”
“አጣርሰኻል። ምስክር ይጠራብኝ ወይንም አይጠራብኝ ነበር
መልሱ።”
“ኸጥያቄህ አልወጣሁም። እማኞች ይጠሩልኝ” እያለ ወደ ሰዉ ተመለከተ ኩቾ።
“አጣርሷል! አጣርሷል! በቅሎዋን ይክፈል!” አለ፣ ሰዉ።
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ለአመጥ መሣሪያ አላነሳህም?”
“ራስ ተስፋ ኢየሱስና ቢትወደድ ስኩት ጃንሆይ ያስሩኻል ቢሉኝ
መሣሪያ አነሳሁ።”
“ተጠየቅ!”
“ልጠየቅ!”
“ምንም ሳታደርግ ጃንሆይ ስለምን ያስሩኻል? ሞተዋል ብለህ
ስላስወራህና ኸወህኒ ነጋሢ ልታመጣ ስለፈለግህ ነው እነራስ ተስፋ ኢየሱስ ያስሩኻል ያሉህ።”
ኩቾ ወደ እፄ በካፋ ተመለከተ። ሁለት እጆቹን ዘርግቶ፣ “ጃንሆይ
ይማሩኝ” ብሎ አጎነበሰ።
“ምትጠይቀው ጥያቄ አለ?” ሲል ጠየቀው አንደኛው አዛዥ ።
“የለኝም። ምሕረት ያርጉልኝ ጃንሆይ!” አለ፣ ኩቾ፣ አጎንብሶ።
ከአዛዦቹ አንደኛው ጋቢውን አስተካከለና ወደ ንጉሠ ነገሥቱ
ተመለከተ፣ “ጃንሆይ ኩቾ የቀረበበት ክስ ክህደት ነው። ክህደት ደሞ በሞት ያስቀጣል” አለ፣ ፍትሐ ነገሥቱን እያገላበጠ። “ፍታ ነገሥቱ ሚለው በንጉሥ ላይ ያመጠና ያሳመጠ በሞት ይቀጣ ነው።”
ይህን ዓይነቱ የሞት ብይን ይገባዋል አይገባውም፤ ወይንም ደግሞ ሌላ ቅጣት ይቀጣ ብለው ለመወሰን መኳንንት እንደየማዕረጋቸው እየቆሙ ከዝቅተኛው ጀምሮ እስከ ከፍተኛው ድረስ አስተያየት ሰጡ።
“ክህደት ነውና ሞት ይገባዋል!” አሉ፣ አንደኛው መኰንን።
“ግዞት ይላክ!” አሉ፣ ሌላው።
“በግርፋት ይቀየርለት!” ብለው ተቀመጡ፣ አንደኛው
“ጃንሆይ መሐሪ ናቸውና ምህረት ይደረግለትና ሹመቱን ይገፈፍ”
አሉ፣ ሌላኛው።
እንደዚህ እያለ ሁሉም ተናግረው ከጨረሱ በኋላ፣ የማሳረጊያው
ንግግር የንጉሠ ነገሥቱ በመሆኑ፣ አፈ ንጉሡ አጎንብሶ ጆሮውን
ሲሰጣቸው ሁሉም ለመስማት ጆሯቸውን ሲያቀኑ ኩቾና ተከታዮቹ
ትንፋሻቸውን ውጠው ተጠባበቁ። ይህን ሁሉ በአንክሮ የምትመለከተው ምንትዋብም ተጠባበቀች።
👍20🤩1