አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
572 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ምንትዋብ


#ክፍል_አስራ_ሶስት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

....ምንትዋብ ማረፊያ ክፍሏ ቆይታ ማታ ላይ ራት ከበላች በኋላ፣ በሁለት ደንገጡሮች ታጅባ ወደ አፄ ፋሲል ቤተመንግሥት አቀናች። ደረጃውን ከወጡ በኋላ፣ ሁለት ያደገደጉ ደጅ አጋፋሪዎች መግቢያው በር ላይ ቆመው ለጥ ብለው እጅ ነሥተው መግቢያው ላይ ባለው በወንዶች የግብር አዳራሽ በኩል እንዲሄዱ መሯቸው።

ምንትዋብ ቆም አለች።

የግብር አዳራሹ ወለል ከፋርስ በመጣ ምንጣፍ አሸብርቋል። በክፍሉ ዙርያ ያሉት ባለመስተዋት መስኮቶች በሐር መጋረጃዎች ተሸፍነዋል ::በፋና ወጊዎች የተለኮሱት በየማዕዘኑ የተቀመጡት ትልልቅ ጧፎች
ክፍሉን አድምቀውታል።

ምንትዋብ ባየችው ሁሉ ተማረከች።

ሴቶቹ ግብር አዳራሽ ስትገባ ተመሳሳይ ድምቀት አይታ ሦስተኛ
ደርብ ላይ ወደሚገኘው የንጉሠ ነገሥቱ መኝታ ክፍል ለመግባት ደረጃ ስትወጣ፣ ደንገጡሮቹ እጅ ነሥተዋት ከኋላዋ ተመለሱ።

ደረጃውን ወጥታ ስትጨርስ፣ አፄ በካፋ ቀን አድርገውት የነበረውን
ዘውዳቸውንና ካባቸውን አውልቀው፣ ማምሻ ክፍል ውስጥ፣ ቀይ ከፋይ የለበሰ ሰፊ ወንበር ላይ ተቀምጠዋል። ከፊት ለፊታቸው ያለ ጠረጴዛ ላይ፣ ጠጅ በብርሌ ተቀምጧል። በክፍሉ ጥግ ጥግ የቆሙ፣ ረጃጅም
መቅረዞች ላይ የተቀመጡት ማሾዎች ለክፍሉ ልዩ ውበት ሰጥተውታል።

አፄ በካፋ፣ ምንትዋብ ስትገባ፣ በፈገግታ ተቀብለዋት፣ ከጎናቸው
ያለ ወንበር ላይ እንድትቀመጥ በእጃቸው አሳይዋት። ስትፈራ ስትቸር ተቀመጠች። ዐይናቸውን ማየት አቃታት።

እሳቸው ግን በእዚያ ምትሐታዊ ውበቷ ዳግም ተማርከው ዐይናቸውን ከእሷ ላይ ማንሳት ተስኗቸዋል። ወዲያው ግን መርበትበቷን አስተውለው፣
“አይዞሽ የኔ ዐይናማ፤ ምንም ሚያስፈራ ነገር የለም እኮ” አሏት፣ እጇን እጃቸው ውስጥ አድርገው።

አቀርቅራ ዝም አለች።

“ያረግሽልኝን ሁሉ መቸም አልረሳውም። ኸኪዳነ ምሕረት ጋር አስታመሽ አዳንሽኝ። የልዥ አዋቂ። ኪዳነ ምሕረት ታክብርሽ።
እንዳው ነገሩን ሁሉ ሳጤነው... እዝጊሃር እንድንገናኝ ፈልጎ ነው እንጂ ኸናንተ ቤት ታምሜ መምጣቴ ተጎድቸ ነበር፤ ኪዳነ ምሕረትና ሩፋኤል እንዳንቺ ባለች ዐይናማ ካሱኝ” አሉ፣ በሠርጋቸው ማግስት ስለሞተችው ሚስታቸው አስበው።

ምንትዋብ እጇን እያፍተለተለች ዝም ብላ አዳመጠቻቸው።
በተናገሩት ነገር ልቧ ተነካ። እኛ እንደዛ በወርቅና በዕንቁ ተንቆጥቁጠው፣ሩቅ ይመስሉ የነበሩት ንጉሠ ነገሥት እንደ እሷው ሰው መሰሏት።

“እስቲ ያነን ሚጥም ድምጥሽን አሰሚኝ፤ ተጫወቺ እስቲ። ኸናንተ
ቤት ሳለሁ ላነጋግርሽ እየፈለግሁ ማን መሆኔ እንዳይታወቅ ብየ ዝም አልሁ። ኸኛ ኸደግ አባትሽ ጋር ስንኳ ሳልጫወት ተመለስሁ” አሏት።

የምትለው ጠፋት። በመጨረሻ፣ ቁስቋም ታክብርልኝ። ለዝኽ
ላበቁኝ ለርሶም፤ እሷው ምላሹን ትስጥዎ” አለቻቸው።
“እኔ ምን ለዝኸ አበቃሻለሁ። ሁለተኛ እንዲ ስትይ እንዳልሰማ።
ሚገባሽ ቦታ ነው የመጣሽ። እኼ ደሞ ቤትሽ ነው፤ ቀስ እያልሽ ሁሉን ትማሪያለሽ። ሚቸግርሽ ነገር ሲኖር ሳትፈሪ ንገሪኝ። ደንገጡሮችሽም አሉ። ለኔም ኸንግዲህ ኻንቺ ሌላ ሚቀርበኝ የለም” አሉና ቀስ ብለው
ተነሥተው፣ ቀኝ እጇን ይዘው፣ መኝታ ክፍል ውስጥ ይዘዋት ሲገቡ፣ በአጎበር የተሸፈነውን ተደራራቢ የእንጨትና የጠፍር አልጋ ስታይ፣ ልቧ ተንተረከከ።

ይሁን እንጂ፣ ልጅነቷ ማክተሙን ብቻ ሳይሆን፣ የዚያን ዕለት
የጀመረችው ግንኙት ሕይወቷ የሚጓዝበትን መንገድ ዳግም እንደጠረገ አላስተዋለችም።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

“ዕድል ኸሰማይ አይወድቅም።”

ሰኞ ጠዋት ጥላዬና አብርሃ አለቃ ሔኖክ ቤት ሲደርሱ ባለቤትየዋ
ወጥታ ተቀበለቻቸው። ውስጥ ሲገቡ ሰባዎቹ መጀመሪያ ያሉ፣
የግርማቸው፣ የብልኅነታቸውና የደግነታቸው ድባብ የሚያስተጋባ
አዛውንት መደብ ላይ ተቀምጠው ብራና ላይ የተጻፈ ጸሎት ያነባሉ።
የጥምጥማቸው ንጣት አካባቢውን ደመቅ አድርጎታል።

“የዠመሩትን እስቲጨርሱ ነው። ዐረፍ በሉ” አለቻቸው ባለቤቲቱ፣
ከአለቃ ሔኖክ ፊት ለፊት ያለ አጎዛ ጣል የተደረገበት መደብ በእጄ
እያሳየቻቸው።

ጥላዬ፣ አለቃ ሔኖክን በፈገግታ ከላይ እስከታች ተመለከታቸው።
ቀልቡ ወደዳቸው፣ ከእሳቸው ዘንድ ጉዳዩ እንደሚቃናለት አንዳች ነገር ነገረው። ከእሳቸው ሌላ ማንም ባያስተምረው ፈለገ። ቤቱን ሲቃኝ፣ ጥግ ላይ ካለው የጠፍር አልጋ በስተቀር እምብዛም ዕቃ አይታይበትም።ከአልጋው ግርጌ የቀለም ቀንዶች፣ የቀርከሀ ስንጥሮች፣ ብራናና በዕራፊ
ጨርቅ የተጠቀለሉ ዱቄት መሳይ ነገሮች ተቀምጠዋል። ይህንን
እየተመለከተ ሳለ አለቃ ሔኖክ፣ “አድራችሁ ነው ልጆት?” ሲሏቸው
ከአብርሃ እኩል ብድግ ብሎ ለሰላምታቸው የአክብሮት ዐጸፋ መለሰ።

“ምን ፈልጋችሁ ነው?” በሚል ዓይነት ሲያይዋቸው አብርሃ፣ “እሱ
ኸቋራ ነው የዘለቀ። ሥዕል መማር ፈልጋለሁ ቢለኝ ኸርሶ ዘንድ
ይዠው መጣሁ” አላቸው።

“መልካም... ሥዕል ለመሣል ቅኔ መማር አለብህ። ሞካክረኻል?”
“ወፍታ ጊዮርጊስ የንታ አምሳሉ ዘንድ ሥላሤ አድርሽ... ወዲህ
መጣሁ።”
“ሥዕል ሥለህ ታውቃለህ?” አሉት፣ ትክ ብለው እያዩት። ዞር አሉና፣ ምድጃ ላይ ድስት ጥዳ የነበረችውን ባለቤታቸውን፣ “ወርቄ እስቲ ሚቀመስ ታለ፤ ለዛሬ ዕንግዶቻችን ናቸው እኒኸ ተማሮች” አሏት።

ጥላዬ፣ ለጠየቁት ጥያቄ አዎም የለም አልሣልኩምም ማለት ፈለገና አመነታ። ዐይናቸው እሱ ላይ ተተክሎ ሲቀር፣ “ጥቂት ሞካክሬአለሁ፤ ግና ብራና ላይ ማይዶል” አላቸው።

“ዛዲያ ኸምን ላይ ሣልህ?”
ሊናገር ፈልጎ ዐፈረ። እሳቸው መልስ ፈልገው ተጠባበቁ። ያን
ችምችም ያለና ወተት የመሰለ ጥርሱን ብልጭ አደረገና፣ “ግድግዳ
ላይ” አላቸው።
“ግድግዳ ላይ? ግድግዳ ላይ እኮ ማነም ተነሥቶ አይሥልም።”
እንጀራ በድቁስና ጠላ ይዛ የመጣችው ወርቄ ከት ብላ ሳቀች። ያን ጊዜ ሁሉም፣ አለቃ ሔኖክ ጭምር ሳቁ። ጥላዬ፣ ወርቄ ጠላውን መጀመሪያ
ለአለቃ ሔኖክ ከዚያም ለእሱናኸ ለአብርሃ ቀድታ እስክታስቀምጥ
ጠበቀና፣ “ኸቤታችን ግድግዳ ላይ ነው። በእናቴ ወንፊት ዐመድ
እየነፋሁ፣ በውሃ ለቁጨ ሳበቃ ኸቤታችን ዠርባ ግድግዳ ላይ በእናቴጸ አክርማ እሥላለሁ። አባቴ ሲያዩት ይቆጣሉ። ግድግዳውን መልሰው
በጭቃ ያስመርጉታል” አለ።
ወርቄ እንደገና ከት ብላ ሳቀች፤ ሁሉም አብረዋት ሳቁ። ጥቂት
ቆይታ በድቁስ ከቀረበው እንጀራ ላይ ግማሹን ተቃምሰው መተዋቸውን ተመልክታ ለጠላው ማጣጫ በአነስተኛ ጮጮ ላይ ቆሎ ይዛ መጣች።

አለቃን አዘግናቸው እነጥላዬን፣ “እየቆረጠማችሁ” ብላ አስቀምጣላቸው ሄደችው ።
አለቃ ሔኖክ ከዘገኑት ቆሎ ላይ ቆንጠር አድርገው አፋቸው
አደረጉና፣ “ሥዕል መሣልህ ነው ወይስ ግድግዳ ላይ መሣልህ ኣባትህን ሚያስቆጣቸው?” ሲሉ ጠየቁት።

“ወታደር መሆን አለብህ እያሉኝ... ሥዕል እንድሥል አይፈልጉም።
በቅኔውም ቢሆን እንድገፋ አይፈልጉም። እሳቸው እስታሉ ድረስ አገሬ አልመለስም ብየ ጠፍቸ ወዲህ ዘለቅሁ።”

አለቃ ሔኖክ ራሳቸውን ነቀነቁ፣ መሆን የለበትም በሚል ዓይነት።
“ላባትህ መልክትም ቢሆን ላክባቸው። ያዝናሉ። እናትህም ቢሆኑ በልቅሶ ይሞታሉ። ብዙዎቻችን ለትምርት ብለን ጠፍተን ነው ኸቤት ምንወጣ ግና ኋላ እንመለሳለን። አባትህ ላንተ ሌላ ተመኙ፣ ከንተ ደሞ ሌላ ፈለግህ። ክፋት የለውም። ባባትህ ቂም እንዳትይዝ። ለማንኛውም
👍16
ሥዕል መሣል ፈልገህ እዝኸ ድረስ መምጣትህ ለሥዕል ያለህን ፍቅር
ያሳያል። እኔም እንዲህ ያለውን ተማሪ ነው ምወድ።”
“ባባቴስ ቂም አልይዝም። ለግዝየው ሥዕል አላሠራ ቢሉኝ
ተቀየምሁ እንጂ። የንታ ታዛዥዎ ነኝ። ሲያመቸኝ ኸጀ አያቸዋለሁ”
ኣለና ተነሥቶ እጅ ነሣ፡፡
“እንግዲህ ...” አሉት አለቃ ሔኖክ። “ሥዕል ስትሥል ኸየት ዠምረህ ወዴት እንደምትኸድ ማወቅ አለብህ። መዠመሪያ እጅህን ታፍታታለህ።
ኸዚያ በኋላ ዓለማውያንን... ቄሱን፣ መነኩሴውን... የመሳሰሉትን ትሥላለህ። ቀጥለህ ጻድቃንን፣ ኸዚያ ሰማዕታትን ትሥላለህ። እነዝኽ በግብራቸው ቢለያዩም ለባስያነ ሥጋ ወይንም ሰዎች ናቸው። እነዝኽን
ከሣልህ በኋላ መላዕክትን ትሥላለህ። ከዚያም የፍጡራን ሁሉ ፈጣሪ የሆነውንና ለዝች ዓለም ቤዛ ሆኖ የመጣውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ውልደት፣ ሥነ-ስቅለትና ጌታችንን የወለደችልንን ድንግል
ማርያምን ሥዕለ ማርያምን... ትሥላለህ። እመቤታችን ንፁህ ናት።

ለመላዕክት የቀረበች ናት። ከፍታዋም የጌታችን ማደሪያ... ማህደረ መለኮት መሆኗ ነው። ሌላውን ስትደርስበት ትማራለኸ አሁን እጅህን ለማፍታታት በጥቁር ቀለም እኩያኖቹን... እባብ፣ ቁራና ሳጥናኤል የመሳሰሉትን በመሣል ትዥምራለህ።”

“ሳጥናኤልን በጥቁር ቀለም?” አለ ጥላዬ፣ ከተቀመጠበት ተነስቶ፡
“አዎ! ምነው?” አሉት፣ ሊል የፈለገውን ጠርጥረው::
“ትናንት ኸደብረብርሃን ሥላሤ ግቢ ውስጥ ኻንድ መነኩሴ ጋር
ስንጨዋወት፣ ሥዕል መማር ፈልጌ ኸቋራ እንደመጣሁ ነግሬያቸው አሉኝ። አንደኛ ሳጥናኤልም ቢሆን መልዐክ ነበር። መላዕክት ደሞ .
በወሬ በወሬ ጥቁር ስለምን የሳጥናኤል መገለጫ እንደሚሆን አይገባኝም ፍጥረታቸው ኸብርሃንና ኸነፋስ ነው። ብርሃን ነጭ ነው። ነፋስ ደሞ ቀለም የለውም። እሱም ቢሆን ብርሃን ተሸካሚ ነበር። በዝኸ ላይ ደሞ
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኸጥቁር ተወልጀ ኸጥቁር አስራ ሁለቱን
ሐዋርያት አመጣለሁ ብሏል እና ጥቁር ስለምን የከሀዲያን... የርኩሳን መገለጫ ይሆናል ሲሉ ነበር።”

አለቃ ሔኖክ ፈገግ አሉ። “እንደሱ ሚሉ አሉ። አየህ ኸጐንደር
ነገሥታት ዘመን ዠምሮ በርካታ ጥያቄዎች ተነስተዋል፤ ክርክሮችም ተደርገዋል። ከእነዝኸ መኻል አንዱ እኼ ነው። ለማንኛውም አሁን አንተ ሥዕል ልትማር ነው የመጣኸውና እኔ ደሞ ማስተምርህ የተማርሁትን ነው። ደሞስ ነፋስ ቀለም የለውም ያለ ማን ነው? 'እስመ ነፋስ ጸሊም በአርአያሁ' ይል የለምን? የነፋስ መልኩ ጥቁር ነው ማለትም አይደል?”
“ኧረ እኔ እሳቸው ሲሉ ብሰማ እንጂ ምኑን አውቄ!” አለና
ከተቀመጠበት ተነሥቶ፣ “ጥሩ ሠዓሊ ለመሆን ስንት ዓመት ይፈጃል?” ሲል ጠየቃቸው።
“የሰነፍ ተማሪ ጥያቄ ነው ይኸ። ለመጨረስ እሚቻኮል ተማሪ ጥበብ አይዝም። ጥበብ ትዕግስትን ትሻለች። በቀጠሮማ ከቶም አትገኝ።

ለማንኛውም ለዛሬ በእንግድነትህና ኸቋራ እዝኸ ድረስ በመዝለቅህ እነግርሃለሁ። የሥዕል ጥበብ እንደ ተማሪው ትጋት ነው እሚያዝ።
ይልቁንም ወደ ቅኔ ሳይቀርብ አይቀርም ምሳሌው። ቅኔ ማለቂያ
የለውም። እንዲያው መምህሩ ተማሪውን 'አሁንስ ይበቃዎታል፣ ኸኔ ያለውን ምሥጢር ወስደዋል፤ ይኸዱና ያስተምሩ' ብሎ መርቆ ይሰደዋል እንጂ። ተማሪው አልጠገብኩም ካለ ይቆያል፤ አለዚያም እሌላ መምር
ዘንድ ኸዶ ይገባል እንደገና። አስተምራለኹ ካለም ወንበሩን ዘርግቶ በያዘው ጥበብ ያነኑ እያስፋፋ ያስተምራል። ሥዕል ክፍልህ ተኾነና ተግተህም ኸያዝኸው ዋና ዋና ጥበቡን ተሎ ትይዛለህ።”

ትኩር ብለው አዩት። ወደ አብርሃም ዞር ብለው መልሰው ዐይናቸውን ጥላዬ ላይ አሳረፉ።
“አስቀድመህ” አሉት፣ “አስቀድመህ እጅህን እያፍታታህ ንድፍ ትማራለህ። ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብም ዋናው ትምህርትህ ነው። ቅኔ ብቻ ሳይሆን፣ ታሪክና አዕማደ ምሥጢር ማወቅ ይገባል።

የብሉይና የሐዲስ ታሪኮች እንደሐረግ የተሣሠሩ ናቸው፤ የብሉይ ነቢያት ለሐዲስ ሐዋርያት አርአያ ይኾናሉ። ስለዝኽ ነው መጽሐፍ ቅዱስን ሳያውቁ ሥዕል መሣል እማይቻለው።”

ወደ ባለቤታቸው ዞር ብለው፣ “ወርቄ ኸጠላው ቅጅላቸዋ” አሏት።ወርቄ ጠላውን እስክትቀዳ ጠብቀው ስትሄድ፣ “አየህ ልዣ” አሉት ጥላዬን ትኩር ብለው እየተመለከቱት። “ሥዕል መሣል ማለት የአንድን ሥዕል ንድፍ ማወቅና ብራና ላይ አሳምሮ መገልበጥ ብቻ አዶለም።
ብዙ ማወቅ ያለብህ ነገር አለ። ስለምትሥለው ነገር ምሥጢሩን
ማወቅ ያስፈልጋል። ከባዱ ነገርም እኼው ነው። የምትሥለውን ሥዕል
ታሪክ ማወቅም ብቻ ሳይሆን ሥዕሉ ቤተክሲያን ውስጥ የሚሣልበትን ቦታ…. በግራ ይሁን በቀኝ..እ... ሚሣልበትን ቀለም ሁሉ ጠንቅቆ ማወቅ ይገባል። ምትለውን ሥዕል እንደ ተሣዩ ማንነትና ታሪክ ምትመርጠው ቀለም ይለያያል ማለቴ ነው። ጽፈትህ... አጣጣልህ
እንዴት ነው?”
“የንታ ኣምሳሉ መልካም ነው ይሉኝ ነበር።”
“ማለፊያ።”
አብርሃ፣ ከተቀመጠበት ተነስቶ።
“አለቃ ጥላዬ ማደሪያ የለውም።

ኸደጀሰላም ነው ሚያድር” አለ
“ጥሩ ግዝየ መጥተሃል” አሉት፣ ጥላዬን እያዩ። “ኸኛ ዘንድ ይኖር
የነበረ ተማሪ በቅርቡ ትምርቱን ኸኔ ዘንድ ጨርሶ ወደ ደብረ ወርቅ
ኸዷል። እኔም ባንዳንድ ነገር ሚረዳኝ ሰው ስለምፈልግ በጓሮ አንዲት የተማሪ ጎገር ምታህል ቤት አለችኝ። ኸዛ ትቀመጣለህ። የዕለት ጉርስህን አንነሳህም። ዛሬም ቢሆን ከኛ ዘንድ መጥተህ ማደር ትችላለህ።”

ጥላዬና ኣብርሃ፣ ሊሄዱ ሲነሱ ወርቄ፣ “ወጡ ደርሷል፣ ሳትበሉማ
አትኸዱም” አለቻቸው። ተመልሰው ተቀመጡና ምሳ በልተው፣ አለቃ ሔኖክን እጅ ነሥተው ወርቄን አመስግነው ወጡ።

ጥላዬ፣ ሥዕል የመማር ዕድል ማግኘት ብቻ ሳይሆን፣ ጎኑን ማሳረፊያ ቤት ማግኘቱ አስደሰተው። ዕድል ለመጀመሪያ ጊዜ በእሱ ጎን የቆመች መሰለው። ሕልሙንና ምኞቱን ሊያጨናግፉበት የሞከሩትን አባቱን ይቅር አላቸው። አባቴ እስታሉ አገሬ አልመለስም ያልሁትን ሁሉ እዝጊሃር ይቅር ይበለኝ። እናቴ፡ “ዕርቅ፣ ደም ያደርቅ” ትል የለ? አለቃ ሔኖክም ቢሆኑ ባባቴ ቂም እንዳልይዝ መክረውኛል። እኔም
ቃል እገባለሁ። አባቴ ባሉበት ደሕና ይሁኑ። እዝጊሃር ያለ ቀን ኸጀ አያቸዋለሁ አለ፣ ለራሱ።
የኔና የወለቴ ነገር ገና ሳንወለድ ተጥፎ የተቀመጠ ይመስለኝ ነበር።

የእዝጊሃር ነገር ይገርመኛል። ባንድ እጁ ሰጥቶ በሌላው ይነጥቃል።
ወለቴን ለሌላ ሰጥቶ ለኔ ሥዕል ሰጠኝ። ሁለቱንም ቢሰጠኝ ይከብደው ኑሯል? ወይስ ዕጣ ፈንታዬ ወለቴ ሳትሆን ሥዕል ብቻ ኑሯል?
ኸዝጊሃር አልጣላ መቸም። ለነገሩ ነው እንጂ እኔ እንደ ንጉሥ ላኖራት
አልችል። ለማንኛውም እሱ ባለቤቱ ያውቃል፤ ምስጋና ይግባው።

ጐንደርም ትባረክ! ዕድል ተርታየን አበጃጀችልኝ፡ እንደኔ ያሉት
መጥተው አይፈሩባት ሲል አሰላሰለ።

ከሐሳቡ ሲመለስ አብርሃ ከጎኑ ይራመዳል። “በደስታ አሳብ ይዞኝ
ጭልጥ አለ” አለው።

“አይቸህ እኮ ነው ዝም ያልሁት። ደካክሜአለሁ ይበቃኛል ሲሉ
የነበሩት የንታ አንተን ሳያቅማሙ ተቀበሉህ። ኣንዳች ያዩብህ ተስፋ
አለ። መምህራን እንዲህ በአንድ ቀን ትምህርቱንም ማደሪያውንም
ቀለቡንም እሰጥሃለሁ አይሉም፤ እንዲያው አንዳች ብርቱ ሆሳዕና
ይዘሃል መሰለኝ” ሲል ቀለደ።

“አየ! ትምህርቱን በውል ሳልይዘው መድኃኒቱንና አስማቱን በየት ደርሼበት ብለኽ? ሆሳዕና ለእንደኔ ላለው ማን ያሳያል ብለኽ ነው? ባይኾን ያንተ ሆሳዕና ሳይኾን ይቀራል እንዲኽ ግንባር የሰጠኝ?” ሲል ቀልዱን በቀልድና በምር አዋዝቶ መለሰ ጥላዬ።
👍7
“አረ ቆይ እስቲ፤ እንዲያው ቀልዱ ይቈየንና አለቃ ኻሉት ውስጥ
የገረመኝ እጅህን ምታፍታታው ክፉ ክፉውን በመሣል ነው ያሉት
ነው። ለመሆኑ ሳጥናኤልን እንዴት አርገህ ልትሥለው ነው? መክሥተ
ኣጋንንት ልትደግም?” አለ አብርሃ “መክሥተ አጋንንት ልትደግም”
የሚለው አባባሉ ራሱን ሳይቀር እያሳቀው።

“በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ! የምን መክሥተ አጋንንት
አመጣህብኝ ወንድሜ! እንዲያው ክፉ ሰው አስመስየ ቁጭ አላረገውም እንዴ! ዐይኑን ያጐረጠ፣ ገባሮውን እንደ ቀንድ ያሾለ፣ ጥርሱን እንደካራ የሳለ አድርጌ ብሥለው ማንነቱ ግልጥ ነው። እንግዲያማ እሱን በድግምት በዐይነ ሥጋ አይቼ ብሥለው ሚካኤልን በምን ላየው
ነው? ከቶስ ሥላሴን በምን አስማት ላያቸው እችላለሁ? ሥዕል ግብርን እንጂ መልክን ሚከተል አይመስለኝም። እደብረብርሃን ሥላሤ ውስጥ ያየኋቸው ድንቅ ሥዕሎች ቅዱሳኑንም ሆነ ርኩሳኑን በዐይነ ሥጋ በተመለከቱ ሠዓሊያን አይደለም የተሣሉ። ቅድም የንታ እንዳሉት ታሪካቸውን፣ ገድላቸውን፣ ተአምራታቸውን ወይም እኩይ ግብራቸውን ባነበቡ ሠዓሊያን እንጂ' ብሎ ያንን እየቆጠበ የሚሰጠውን ፈገግታውን
አሳየው።

አብርሃ ተፍለቀለቀ። “ድንቅ ብለኻል፤ መምሩ ዛዲያ ምን ሊነግሩህ ሰይጣንን ስትሥለው ቁመቱን ኣለቅጥ ረዥም አርገው። ሰይጣን ከሀዲ ነው በል ይኸን ኹሉ ኻወቅህ?” አለና ቀልዱን በመቀጠል፣ “ለማንኛውም
ነው፣ እባብ አሳሳች ነው... ቁራ ምንድር ነው?” ሲል ጠየቀው።
“ሚመስለኝ ያው ቁራ አይታመንም። ተልኮ ሳይመለስ የቀረ በዋል ፈሰስ ማዶል?”
“ውነትህን ነው። እስቲ ጃን ተከል ወረድ ብለን ጥቂት ወሬ
እንቀላውጥና እኔም ወደ ቅኔየ ልኸድ።”
ጥላዬ ግን መሄድ አልፈለገም። የሰሞኑ ወሬ የምንትዋብ መምጣት በመሆኑ ሰምቶ ልቡን እንደገና ማድማት አልታየውም። ግን ደግሞ ያን ሁሉ ውለታ የዋለለትን አብርሃን ማስቀየም አልፈለገም።.....

ይቀጥላል
👍11
አትሮኖስ pinned «#ምንትዋብ ፡ ፡ #ክፍል_አስራ_ሶስት ፡ ፡ #ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ ....ምንትዋብ ማረፊያ ክፍሏ ቆይታ ማታ ላይ ራት ከበላች በኋላ፣ በሁለት ደንገጡሮች ታጅባ ወደ አፄ ፋሲል ቤተመንግሥት አቀናች። ደረጃውን ከወጡ በኋላ፣ ሁለት ያደገደጉ ደጅ አጋፋሪዎች መግቢያው በር ላይ ቆመው ለጥ ብለው እጅ ነሥተው መግቢያው ላይ ባለው በወንዶች የግብር አዳራሽ በኩል እንዲሄዱ መሯቸው። ምንትዋብ ቆም አለች። …»
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሰላሳ


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


...የሰሜን ኢትዮጵያ የእርስ በርስ ጦርነት ድምፁ እየበረከት ሄደ። ተፋላሚ ወገኖች ዜናቸው ሁሉ የሞት ሆነ፡፡ ለወደፊቷ ኢትዮጵያ ገዢነት መወዳደሪያው በገደሉት ሰው ቁጥር እንዲሆን የተወሰነ ይመስል የአንዱ ወገን ራድዮ
"አንድ ሺ ገደልኩ"ካለ ሌላው ወገን ማታ ላይ "ሁለት ሺ ገደልኩ ይላል፡፡" በየቀኑ እንዲሁ ይቀጥላል፡፡ የሚገለፀው የሟች ቁጥሩ ከዕለት ወደ ዕለት እየበዛ ሄደ መንግስት በሁለት ግንባር ሰርጐ ገቦችን ደመሰስኩ» ሲል አማፂያን ደግሞ አራት
ቦታዎችን ከፋሽስት የጭቆና አገዛዝ ነፃ አወጣን ይላሉ። በየቀኑ ተመሳሳይ ወሬ ሀገሪቱ ምድሯ ብቻ ሳይሆን እየራም በደም ተለወሱ። በመግደል ውድድር
በመገዳደል ዜና! በመጨራረስ አባዜ።
የሀገራቸውን እውነተኛ ዜና መዋዕል በራሳቸው ሀገር የዜና አውታሮች ለመስማት ያልታደሉ ኢትዮጵያውያን ሁለቱንም ወገኖች አያምኑም፤ የውጭ ራዲዮዎችን መጐርጐር ግድ ብሏቸዋል። እነዚያም ቢሆኑ አንዳንዴ መንግስት እንዲህ ይላል፣አማፂያን ደግሞ እንዲያ… ነገር ግን በገለልተኛ ወገን አልተረጋገጠም
ይሉና የሕዝብ ልብ ያንጠለጥላሉ፡፡
አንድ ነገር ብቻ ግልጽ ነው፤ በሰሜናዊ የሐገሪቱ ክፍል በየቀኑ ጦርነት አለ። በየቀኑ መድፍና መትረየስ ይተኮሳል፡፡ በየቀኑ ሰው ይሞታል። በየቀኑ ሀገር
ትደማለች:: በየቀኑ ንብረት ይወድማል። ከቀን ወደ ቀን አንጡራ ሀብቷ ይቀንሳል። በየቀኑ የህዝብ ስቃይ አለ። በየቀኑ ዋይታና ጩኸት አለ፡፡
የአስቻለው ትዝታ ለዲላ የፍቅር ቤተሰቦቹ የሚደርስው በዚሁ የሰቆቃ ሽቴ እየተላወሰ መሆን ከጀመረ ሰነበተ ስጋትና ፍርሀት በሁሉም ልብ ማደር ጀመረ።
የጦርነት ወይም የሞት ዜና በተሰማሩበት ቁጥር አስቻለው በሁሉም አዕምሮ ውስጥ ብቅ
ድቅን ማለቱን ቀጠለ። ይፈሩ ጀመር:: ይጨነቁ ጀመር፡፡
ችግሩ በሔዋን ላይ ጠነከረ። ሳትወድ በግድ ራድዮ ጉርጓሪ ሆነች፡፡የምትሰማው ዜና ሁሉ ያስደነብራት ጀመር፡፡ በሆነ ቁጥር ሰው ሞተ ከተባለ ከንዱ አስቻለው እንደሆነ ታስብ ጀመር፡፡ ለእሷ አስቻለው ትናንት ሞቷል፡፡ ዛሬም
ይሞታል፡፡ ነገም እንዲሁ:: ልቧ በፍርሀትና በስጋት ቆሰለ። አንጀቷ በሀዘን ይታጠፍ ጀመር፡፡ ዓይኗ እንባ ከላቋርጥ አለ። በሀሳብ ብዛት የቀን ዕረፍትና የሌሊት
እንቅልፍ አጣች። ለራሷ ሰላም አጥታ ሌሎችንም ሰላም ነሳች፡፡ በሁሉም ዘንድ ወለሌ ሆነ፡፡
በእንቅርት ላይ እንዲሉ ልክ ሚያዚያ ወር መጨረሻ ላይ ከዲላ
ሆስፒታል አካባቢ አስደንጋጭ ወሬ ተሰማ:: የአስቻለው ደሞዝ ተቋረጠ፡፡ በልሁ በውክልናው መሰረት አስቻለው ኤርትራ ከሄደ ጀምሮ ሲቆጠር የአስረኛ ወር
ደመወዙን ሊቀበል ሲሄድ ገንዘብ በእጁ ሳይሆን ለጆሮው መጥፎ ዜና ሰጥተው መለሱት በተላለፈልን ስርኩላር መሰረት ደሞዙ እንዳይከፈል ተብሏል የሚል።
በልሁ ምክንያቱን ለማወቅ አጥብቆ ጠይቆ ነበር፣ ነገር ግን የተሰጠው ምላሽ የመጀመሪያው ደብዳቤ ከአስመራ ሊሆን እንደሚችልና ከዚያ ለዋናው መስሪያ ቤት፤ ቀጥሎ ለሲዳሞ ክፍለ ሀገር እንደገና ለአውራጃው ከዚያም ለዲላ ሆስፒታል ሲተላለፍ አንዱ ለሌላው ላይ ተመስርቶ ሲጽፍ ሲፃፃፍ የታገደበት ምክንያት አንዱ ጋር ተዘንግቶ ሊሆን እንደሚችል ግምታቸውን ከመግለፅ በቀር እቅጩን
አልነገሩትም፡፡ አንድ ነገር ብቻ በግልጽ ነገሩት፤ ከእንግዲህ በአስቻለው ስም ደመወዝ ወጪ ሊደረግ እንደማይችልህ! በልሁ መርዶውን ይዞ ተመለሰ:: ዜናው
ከታፈሡም ከመርዕድም ጆሮ ደረሰ፡፡ የአስቻለው ነገር ከዕለት ዕለት እየራቀ ሄደ።
ይህን ዜና ለሔዋን እንዴት አድርገው ይንገሯት? ዝም አይል ነገር የአስቻለው ደመወዝ የሕልውናዋ መስረት ነው። አይነግሯት ነገር ትሳቀቃለች ብለው ፈሩ።በእርግጥም'' እንደ ቁስል ፈሯት:: የዚያኑ ያህል ታሳዝናቸው ጀመር። ለቀናት ያህል
በሃሳብ ሲታመሱ ሰንብተው ሁሉም ለበጉ ነው የሚለውን ኢትዮጵያዊ ብሂል ለመጠቀም ወሰኑ። ደስ ብሎናል ደስ ይበልሽ፡ የአስቻለው ደሞዝ ተቋረጠ። ይህ
የሚያመለክተው የአስቻለውን በሕይወት መኖር ነው፡፡ ነገር ግን የመንግስት ሥራ ለቋል ማለቴ ነው
በሕይወትህ ባይኖር ኖሮ ጡረታ ወይም ዳረጎት ውሰዱ እንባል ነበር። አስቻለው ዱሮም የከፋው ሰው ነበርና በአስብ ወይም በምጽዋ በኩል ደብዳቤውም በቅርቡ እንደሚደርስን እናምናለን፡፡ ማን ያውቃል? አንቺንም ሊወስድሸ ይችላል፡፡” እያሉ ሊያጽናኗት ተመካከሩ። ቀና ሲታጣ... እንዲሉ ምርጫቸው
ይኸው ብቻ ሆነ፡፡ ይህን ለመፈጸም በግንቦት ወር የመጀመሪያ ሳምንት ላይ ቅዳሜን
መረጡ፣ ሁለም ተሰብስበው በሔዋን ቤት ለመዋልና እየተረዳዱ
የሔዋንን ልብ ሊያደነቁሩ።
በዕለቱ ታፈሡ ከሁሉም ቀድማ ከሔዋን ቤት ስትደርስ ከቀኑ ሰባት ሰዓት ተኩል አካባቢ ሆኗል፡፡ በትልቅ ሳህን ለሁሉም የሚበቃ ምግብ ይዛለች፡፡ ለራሷ
የነጭና የጥቁር ቡራቡሬ ድሪያዋን ለብሳ፣ እዝን አትለው አክፋይ ለሔዋን ደግሞ ለየት ያለች ስክርፍ ገዝታለች፤ ለስጦታ።
ቀጥሎ የደረሰው መርዕድ ነው አውሎ ላያስመሽ የሚችል ምርጥ የጫት ቅጠል ይዞ። የሐረሩ ልጅ መርዕድ የጫት ሥነ ስርዓቱን ያወቅበታልና ሁሉን ነገር
ወዲያው አመቻቸው:: በእሱ አመራር ሰጪነት ሰንደሉ ተሰኮሰ፡ እጣኑ ተጨሰ፡፡ቡናውም በብረት ምጣድ ላይ ይንቸሰቸስ ጀመር። የቤቱ መዓዛ ሙሉ በሙሉ
ተለወጠ። ሥነ ሥርዓቱን ለመጀመር የበልሁ መድረስ ብቻ ይጠብቅ ጀመር፡፡ የጫት
መቃም ልምድም ሆነ ሱስ የሌላት ታፈሡ ያለ ወትሮዋ በመሀል ፍራሽ ላይ ሙሽራ መስላ በመቀመጥ ቤቱን በቀልድና በጨዋታ
ሞልታ በሳቅ እያፍለቀለቀችው ሳለች ድንገት ከውጭ በኩል የሰው ድምጽ ተሰማ:: የሴት
ልጅ ጥሪ ይመስላል፡፡ ሔዋን ቡና እየቆላች ስለነበር ትርፌ ወደ ውጭ ወጣ አለች፡፡
የውጭው በር ላይ አንዲት የአሥራ ሁለት ወይም የአስራ ሶስት ዓመት ዕድሜ ያላት ልጅ ቆማ አየችና ወደ እሷ ተጠጋች፡፡
ከልጅቷ አጠገብ ደርሳ አንገቷን
ከውጭ በር ወጣ አድርጋ ስትመለከት ደግሞ ከልጅቷ ጋር አንዲት በዕድሜ ጠና ያሉ ሴት ቆመው አየች፡፡ ሴትዮዋ ጠይም ናቸው፡፡ የባላገር ሴት ይመስላሉ፡፡
የነጭና አረንጓዴ ቡራቡሬ ቀሚስ ቀነጭ ነጠላ ለብሰዋል። ሳሳ ያለች ሸራ ጫማ አድርገዋል፡፡ ፀጉራቸውን በነጭ ሻሽ ግጥም አድርገው አስረዋል፡፡ እጆቻቸውን
በነጠላቸው ውስጥ አድርገው ወገባቸው ላይ አጣምረው ቆመዋል፡፡
«ምነው?ማንን ፈለጋችሁ?» ስትል ትርፌ ልጅቷንም ሴትየዋንም ተራ
በተራ እያየች ጠየቀቻቸው፡፡
«ሔዋን የምትባል ልጅ እዚህ ቤት ውስጥ ናት?» ስትል ልጅቷ ትርፌን ጠየቀቻት።
«ግን ምነው?" አለች ትርፌ ደንገጥ እንደ ማለት እያለች።
«እስቲ ብቅ በይ በያት»
ትርፌ ግራ ገባ እያላትም ቢሆን ወደ ቤት ተመለሰችና እታለም! አንዲት ልጅና እንድ ተለቅ ያሉ ሴት ይፈልጉሻል፡፡» አለቻት፡፡ ሔዋን ደንገጥ ብላ ቀና በማለት ትርፌን በመመልከት ላይ ሳለች ታፈሡ ቀድማ«ምን አይነት ሴት እማማ ዘነብ ይሆኑ እንዴ?» ስትል ጠየቀች።
«እኔ እንጃ! ብላ ሔዋን ወደ ውጭ አመራቻ፡፡
ወዲያውኑ ልብ የሚሰነጥቅ ጩኸት ተሰማ:: የሔዋን ድምጽ ስለመሆኑ ሁሉም አልተጠራጠሩም። ታፈሡ መርድና ትርፌም በቅጽበት በመነሳት ወደ ውጭ ሮጡ፡፡ ሔዋን የሆነችውን ነገር ሳያውቁ ነገር ግን «ሔዋን አይዞሽ ሔዋን አይዞሽ! እያሉ በመጯጯሁ አጠገቧ ደረሱ
👍8🔥1
ከደረሱ በኋላ እኳ እየተከናወነ ያለውን ነገር በቶሎ ለመለየት ተሳናቸው። ሔዋን በሴትየዋ እግር ላይ ወድቃ እየተንፈራፈረች እማ…! እማዬ! እማይዩ-l በማለት
ትጮሀለች፡፡ ሴትዮዋም በሔዋን ጀርባ ላይ እንገታቸውን አንተርሰው ልጄ እሙ እመዪ!» ይላሉ። የእናትና ልጅ ናፍቆት የፈጠረው ድንገተኛ ትርምስ ኖሯል፡፡
ታፈሡ ፈጥና ወደ ትንቅንቁ በመግባት የእረ ምንድነው? ኧረ እባካችሁ እያለች የሔዋንን እናት ሔዋን ጀርባ ላይ ለማንሳት ስትታገል መርዕድ ደግሞ ሔዋንን
ከአናቷ እግር ላይ ለማንሳት ይፍጨረጨር ጀመር። ትርፌ ግራ ገብቷት ቆማ እናቷ ነኝ ልጆች! እስቲ እሷን እንሶልኝ! እረ እስቲ በርቱልኝ» አሉ ሴትዮዋ እንባቸውን እያዘሩ። ሔዋን እግራቸው ላይ ተጠምጥማ ስትጮህ
ታፈሡና መርዕድ ቀና ሊያደርጓት ሲሞክሩ በልሁ ድንገት ደረሰ፡፡
«ምንድነው ታፈሥ ምንድነው መርዕድ?» አላቸው ድንገጥ ብሎ ዓይኑን ወዲያ ወዲህ እያማተረ።
«ሔዋንን አንሳልን በልሁ። እናቷ ናቸው። ቶሎ በል!» አለችው ታፈሡ ሔዋንን ከእናቷ እግር ለማንሳት እየታገለች።
እጅሬ በልሁ ታፈሡንም መርዕድንም ገፈታትሮ ብቻውን ጐንበስ በማለት ሔዋንን ከእናቷ እግር ላይ ፈልቅቆ አነሳት፡፡ ሔዋን ግን ወዲያው ቀሚሳቸውን
ሙጥኝ አለች:: አሁንም «እማ! እማዬ እማይዬ! በማለት ማልቀሷን ቀጠለች እናቷም «አይዞሽ ልጄ! አይዞሽ እሙዬ!» እያለ እንደ ልጃቸው ያለቅሱ ጀመር።
ሔዋንና እናቷ እንደተነፋፈቁ እናትና ልጅ ሳይሆን በሙጫ እንደተጣበቁ ወረቀቶች ተያያዘው በበልሁና በታፈሡ ግፊት ወደ ቤት ገቡ፡፡ ፍራሽ ላይ ከተቀመጡም በኋላ አንገት ለአንገት ተያይዘው በለቅሶ ይንፈቀፈቁ ጀመር፡፡ ታፈሡ
በልሁና መርዕድ ክፊትለፊታቸው ቆመው ቢለምኗቸውም ቶሎ እሺ አላሉም፡፡በርካታ ደቂቃዎች አለፉ ልጅ እናቱን መውደድ፣ እናት ለልጅዋ መሳሳት እንኩዋንስ በሰው ልጅ በእንስሳትም ዘንድ የታወቀ ነው፤ የሔዋንና የእናቷ ሁኔታ ግን ከተለመደው መጠን በላይ ሆኖ ሲታይ እጀግ ያሳዝን ነበር፡፡ ታፈሡ ወድያው ወደ ፍራሹ ጎንበስ አለችና መርእድ በላስቲክ ጠቅልሎ ለቅሞሽ ያዘጋጀውን
ጫት አቅልሎ አድርጋ በማንሳት ወደ ጓዳ ይዛው ገባች፡፡ ጫቱን አስቀምጣ እንደገና ምልስ አለችና በልሁና መርዕድን በዓይኗ እየጠቀሰኝ ወደ ውጭ ወጣች፡፡ እነሱም ፈጥነው ተከተሏት።
«ምን እናድርግ?» ስትል ጠየቀቻቸው።
በልሁም መርዕድም “ምን ይሻላል? እንዴት እናድርግ የሚል ጥያቄ አከታተሉ። የመጨረሻ ውሳኔያቸው ለሔዋን እናት መስተንግዶ መጣደፍ ነበር፡፡
በዚሁ መሰረት በልሁና መርዕድ ሥጋ እና የመጠጥ ዓይነቶችን ሊገዛዙ ወደ ከተማ ሮጡ፡፡ ታፈሡ ወደ ቤት በመመለስ፡-
«ትርፌ» ስትል ጠራቻት።
«አቤት»
«በርካት አድርገሽ ቡና ቁይ አለቻትና ከሔዋን አጠገብ ፍራሿ ላይ ቁጭ አለች በዚያ ሰዓት ሔዋንና እናቷ ከለቁሷቸው ትንሽ በረድ እያሉ ናቸው፡፡እንባቸው ከዓይናቸው ላይ መፍሰሱን ባያቆምም ከመርገብገቡ ቀዝቀዝ እያሉ ሄዱ ታፈሡ በጨዋታ አሳብባ ስሜታቸውን ለመቀየር አስባ «እንደው ሳይታሰቡ ከየት ብቅ አሉ የእኔ እናት?» ስትል የሔዋንን እናትና ጠየቀቻቸው፡፡
«ምን ላድርግ ብለሽ ነው የእኔ ልጅ፣ ባዳምጥ ባዳምጥ የልጆቼ ድምጥ ጥፍትት አለብኝ፡፡ ባለፈው ክረምት ይመጣሉ ብዬ ስጠብቅ ቅርት እሉ፡፡ በጋውም ይኸው አለቀ፡፡ ሆዴ አልችል ቢለኝ መጣኋኮ አሏት በነጠላቸው ጫፍ ዓይንና አፍንጫቸውን አየጠረጉ።
«ሸዋዬ ደብዳቤ እትጽፍም ነበር?»
«ኧረ እሷ እቲ!»
«አንድ ጊዜ እንኳ?»
«በፍጡም!» አሉ የሔዋን እናት፡፡ በዚህ ጊዜ ሔዋን ባልጋለች በማለት ሸዋዬ የፃፈችው ደብዳቢ ትዝ ብሏቸው ሳይሆን አይቀርም ታፈሡና ሔዋን ተያዩ፡፡
«ለመሆኑ መቼ መጡ?» ስትል ታፈሡ እንደገና ጠየቀቻቸው።
«ትናንት ማታ» አሉና «አንድ አስተማሪ ነኝ ያለ የተባረከ ልጅ የሸዋዬን ቤት አሳይቶኝ እሷ ጋር አደርኩ፡፡»
«እዚህስ ማን አደረሰዎት?»
የሔዋን እናት እንዳጎነበሱ በረጅሙ ተነፈሱና «እንደ አደራረሴ ደረስኩ የኔ ልጅ፣ አይደረስ የለም፡፡» አሏት እዝን ትክዝ ባለ አነጋገር።
ታፈሡ አኳኋናቸውን ልብ ብላ ስታጤን ቆየችና የሔዋን እናት አንድ ደስ የማይል ስሜት በውስጣቸው እንዳለ ተረዳች። ከሔዋን ዙሪያ የማያልፍ መሆኑን
በመገንዘብ ቆረቆራት።ጠይቃ ለመረዳት ስትል “ሔለንን ከሸዋዬ ቤት ሲያጧት ምን ተሰማዎት እማማ?» ስትል ፈገግ ብላ እያየች ጠየቀቻቸው፡፡ በዚያው ሔዋንንም
ሰለል አደረገቻት፡፡ ሔዋን አሁንም በእናቷ ላይ ልጥፍ ብላ እንባዋን ታንቆረቁራለች፡፡
«የእሷንማ ነገር እዚያው አገሬ ሆኜ ሆዴ ነግሮኝ የለ ልጄ፣ ቀድሞም
ተረድቸዋለሁ::አሉና አገጫቸውን በመዳፋቸው ደግፈው ትክዝ አሉ፡፡ ትናንት ማታ ከሸዋዬ ቤት ከደረሱበት ጊዜ ጀምሮ ዛሬ ሔዋን ከአለችበት ቦታ እስከመቼ ደረሱበት ጊዜ ድረስ የነበረውን ሁኔታ በዓይነ ሕሊናቸው ይቃኙት ጀመር።

ልክ እንደ ሔዋን የእናቷ መምጣት
ለሸዋዬም ዱብ እዳ ነበር የሆነባት ስታያቸው ደንግጣ እቅፍ አድርጋ በመሳም በናፍቆት ነበር የተቀበለቻቸው በአክብሮት ጋብዛ ነበር ያስቀመጠቻቸው። ነገር መበላሸት የጀመረው ግን እናቷ ስለ ሔዋን መጠየቅ ሲጀምሩ ነው።
«እሙዬስ የሸዋ?» ሲሉ ነበር የጠየቋት ወድያውኑ እንደተቀመጡ «እሙዬ» የሔዋን የቤት ስሟ ነው «የሸዋ» ደግሞ የሸዋዬ የቁልምጫ መጠሪያ፡፡
«ትመጣለች::» አለቻቸው ሸዋዬ ነገሩን ቀለል አድርጋ፡
የሔዋን እናት ከሸዋዬ ቤት የደረሱት ከአመሻሹ አሥር ሰዓት አካባቢ ነው።ሔዋን ገና እየተማረች መስሏቸው የተማሪዎችን መውጫ ሰዓት ሲጠባበቁ ቆዩ፡፡ነገር ግን እየመሸ ሄደ፡፡ ሔዋን ደግሞ ብቅ አልል አለች። የሔዋን እናት አሁንም
«ይቺ ልጅ ምነው ቀረች የሸዋ?» ሲሉ ጠየቋት።
«ትመጣለች አልኩሽ እኮ» የሸዋዩ አነጋገር ግልምጫ ጭምር ነበር።
አሁንም በጣም መሽ፡፡ ለዓይን ያዘና መብራት በራ። ሸዋዬ ለእናቷ
እንግድነት ቶሎ ቶሎ የሰራችው ወጥ እንደ ደረስ ራት ልታቀርብ
ማስታጠቢያ ይዛ ወደ እናቷ ቀረበች፡፡
«እምዬ ሳትመጣ የሸዋ?»
«ያደረች እንደሆነ ጾምሽን ታድሪያለሽ?»
«እርቃ ነው እንዴ የሄደችው?
ማን ያውቃል? እሷ ራሷ እንደ ልቧ አዳሪ!»
የሔዋን እናት ግራ እየገባቸው ሄደ። እንጀራው ሬት ሬት እያላቸው
ራታቸውን በሉ:: ልባቸው ግን ለሔዋን ተሰቀለ። የሆነችውን ማወቅ አልቻለምና ናፍቆቱ ስጋቱ፣ ጭንቀቱ ሁሉ መንፈሳቸውን አመሰቃቀለው፡- ቆየት ብሎ መኝታ
ሲነጣጠፍላቸው አዩ። ቢያንስ ለዛሬ ሔዋንን ሊያዩዋት እንደማይችሉ አውቀው ።
ደግሞ እንደው ለምናልባቱ በማለት፡
«እሙዬ ማደሯ ነው የሸዋ» ሲሉ ሸዋዬን ጠየቋት፡
«ጠዋት እንፈልጋታለን፡፡»
የሔዋን እናት ሆዳቸው ቅይም አለ። ንዴትም ተሰማቸው፡፡ ግን መታገስ ነበረባቸውና የሆዳቸውን በሆዳቸው አድርገው ለስለስ ባለ አነጋገር፡፡
ምናለ የሸዋ፣ ልጄ የሆነችው ነገር ታለ ነግረሽኝ ቁርጤን ባውቀው
አሏት ዓይናቸውን በሽዋዬ ላይ እያንከራተቱ፡፡
ምን ትሆናለች ብለሽ ሰጋሽ አንቺ?»
«ለምን አልስጋ ልጄ፣ ኧረ ጭንቅ አለኝ የሸዋ!»
«ቁርጡን ልንገርሽ! እሷ እናት፣ እህት፣ ወንድም…. የሚባል ነገር ትታለች:: ሕይወቷን በአሻት መንገድ እየመራች ነው:: ነገ አለችበት ድረስ ትሄጃለሽ: እስከዚያ ድረስ እትጨቅጭቂኝ:: በቃ!» አለቻቸው ሸዋዬ ምንጭቅጭቅ እያለች። የሔዋን እናት አንጀታቸው የባሰውነ ቁርጥ አለ። ቢያንስ ቢያንስ ሁለቱ
👍121
ልጆቻቸው እንደተጣሉ ገባቸው፡፡ ልባቸው ተከፋ፡፡ በተዘጋጀላቸው መኝታ ላይ ልክ እንዳኮረፈ ሰው ኩርምት ብለው ተኙ:: የረባ እንቅልፍ ሳይወስዳቸው በየመሀሉ
እየባነኑ ያ ሌሊት አልቆ በቀን ተተካና ሰማይና ምድር ተላቀቁ፡፡ እየረፈደ ሄደ፡፡ቀኑም ተዳረስ፡፡ ስለ ሄዋን መጠየቃቸውን አቁመው የሽዋዩን እንቅስቃሴ ብቻ ሲጠባበቁ ቆዩ ።
ወደ ሰባት ሰዓት ተኩል አካባቢ ሸዋዪ ከቤት ወጣ ብላ ጥቂት ከቆየች በኋላ አንዲት ኮረዳ ቢጤ ይዛ ተመለሰች፡፡ ልጅቷን ይዛ ፊትለፊታቸው በመቆም «ከዚች
ልጅ ጋር ሂዱ! የልጀሸን ቤት ታሳይሻለች፡፡" አለቻቸው፡፡
የሔዋን እናት «ጎሽ ልጄ እሰይ!» በማለት ሽዋዬን እያመሰገኑ ብድግ አሉ።ሔዋንን እሰሰከዛ ሰአት ድረስ ማየት ባለመቻላቸው ግን አንጀታቸው አርሯል። ከዚያ በኋላ ልጅቷ እፊት እፊት እየመራች ወደ ሔዋን ቤት ወሰዳቸው ነው ልጅ
የልጃቸውን ያህል የሳቸውም ሆድ ባብቶ ያን ያህል ያነቡት።
ይህ ሁሉ ስሜት አሁንም በፊታቸው ላይ ይነበባልና ታፈሡ «ምነው እማዬ»ደስ ያለዎት አይመስሉኝም። የተቀየመብት ነገር ያለ ይመስላል?» ስትል ጠየቀቻቸው።
የሔዋን እናት አሁንም እጎንብሰው ግንባራቸውን እያሻሹ ቢከፋኝስየት
የት ልደርስ ብለሽ የኔ ልጅ! ብቻ እንኳን ልጄን አግኝቼ ዓይኗን ያየሁት» አሉና ወደ ሔዋን ዞር ብለው እያዩዋት እሙ! ደግሞ በአንቺ ሆድ ምን ይኖር ይሆን?» አሉና «አደራ የወላድ መካን እንዳታደርገኝ!» አሏትና ድንገት እንባቸው ድንቡቅ ብሎ ወረደ።
ሔዋንም በዚያው ሁኔታ ተከተለቻቸው፡፡ ታፈሡ በእናትና ልጅ ሁኔታ የእሷም ሆድ እየተንቦጫቦጨ ትንሽ ካለቀሰች በኋላ እንደገና ሁለቱን ማባበሏን ተያያዘችው። ከብዙ ልመና በኋላ ትንሽ በረድ ብለውላት በሀዘንና በትካዜ ዓይን አከታትላ ስታያቸው ሳለች በልሁና መርዕድ ድንገት ከተፍ አሉ፡፡ በሁለት ፊስታል
ዕቃ ይዘዋል። ታፈሡ ተቀበለቻቸውና ወደ ጓዳ ገባች:: ወዲያው የመመገቢያ ትሪና
ያን ከቤቷ ይዛ የመጣችውን ምግብ ይዛ በመመለስ ማቅረብ ጀመረች። በቀይ የሥጋ ወጥ የተፈተፈተ የነጭ ጤፍ እንጀራ ነው።ትሪው ላይ ዘርግፋ ሔዋንና እናቷን ተጨምሮበት ሁሉም ቀርበው እንዲበሉ አደረገች። በልሁና መርእድ ካመጡት ለስላሳ እየከፈተች ማደሏን ቀጠለች።
ታፈሡ በማስተናገድ ሽር-ጉድ ያንን ቤት ሞላችው።
ከምሳ ግብዣው መጠናቀቅ በኋላ ትርፌ ያፈላችው ቡና ተከተለ፡፡ ታፈሡ ፍራሽ ላይ ከሔዋን አጠገብ፣ በልሁና መርዕድ ደግሞ ከፊትለፊታቸው የግድግዳ
ጥግ ይዘው ወንበር ላይ ተኮለኮሉ፡፡ ቡናው ሊቀዳ ሲል ሔዋን እናቷ ከመጡ ወዲህ ለመጀመርያ ጊዜ ተናገረች።
«ጫቱን ተዋችሁት እንዴ በልሀዬ»
«እማማን ፈርተው ይሆናል፡፡» አለች ታፈሡ ፈገግ ብላ ሁሉንም እያየች፡፡
ውይ! ለምን ልጆቼ ሲዳሞ ውስጥ እየኖርኩ ጫት ትጠላለች ብላችሁ
ነው? የራሴ ልጆችስ ምድጃዬን ክብብ አድርገው አይደል ሲቀጨቅጩት የሚያመሹት! እኔንማ አትፍሩ። እንደውም ቤቱ ሲጫጫስ ደስ ይለኛል፡፡» አሉ፡፡
ይደብርዎት እንደሆን ብለን እኮ ነው:: አለ በልሁ ፈገግ ብሎ፡፡
«ኧረ በፍጡም ለምን ልጅ?»

«አምጡት እንግዲው!» አላች ታፈሡ በልሁና መርዕድን በፈገግታ አይን እያየቻቸው።......


💫ይቀጥላል💫
👍132
#ስም_ያለው_ሞኝ_ነው?

ስም ያለው በሙሉ ሞኝ ከተባለ
ሁሉም ባለስም ነው ብልጡ ወዴት አለ
ስም ያው ሞኝ ነው
ሃገሬ ስም አላት ሕዝቧ ስም አላቸው
ባለ ስም ሞኝ ነው ሁሉም ሞኞች ናቸው
ስለዚህም እኔ ሽሽት ጀምሪያለሁ
በሞኞች ሃገር ውስጥ
ብልጥ እንድሆን ብዬ ስሜን ትቼዋለሁ።

🔘ልዑል ሀይሌ🔘
9👍6
#የፍቅር_ግልባጭ

ያኔ ስንገናኝ መንገድ ላይ አስቁሜ
ሁሉም ሰው ስያየኝ ቁልቁል ተዘቅዝቄ
ይሉኝታውን ንቄ
አበባውን ይዤ በዕንባ ተሞልቼ
እየተርበተበትኩ ያልኩሽ አወድሻለሁ
እንዳትሽወጂ 'አፕሪል ዘ ፉል' ነው።

🔘ልዑል ሀይሌ🔘
👍7😱2
#ምንትዋብ


#ክፍል_አስራ_አራት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

...ጃን ተከል ከወትሮው የበለጠ ሰው ተሰብስቦበታል። ወሬው ሁሉ ስለ ቅዳሜው ግብርና ስለ ምንትዋብ ውበት ነው። ቅዳሜ ዕለት ኣብርሃ ቤተመንግሥት በር ላይ የድኃ ተራ እስኪደርስ ጠብቆ ግብር ተካፍሎ ነበርና በአኮፋዳው
ከየዓይነቱ ምግብ ጠቅጥቆ መጥቶ ጥላዬን እንዲበላ
ሲጋብዘው አልበላም ብሎታል።
አብርሃ ምንትዋብን ባያያትም፣
ስለግብሩ ትልቅነት ሲያወራ አልበቃው በማለቱ ጥላዬ ደከመኝ ልተኛ ብሎት ተለያይተዋል።

ጥላዬ፣ ዋርካው ጠርዝ ላይ ቆሞ፣ “ምንትዋብ ብለው ስም አወጡላት እያሉ ወሬውን ሲቀባበሉ ሰማ። አብርሃን ሲያየው ካንዱ ወደ ሌላው እየሄደ ወሬ ይጨልፋል። ምነው እንደሱ የማላውቃት ባረገኝ። ወደ
ቅጥር ውጭ እኔ ዛፉ ስር ቁሜ አንቺ ነጠላ ተከናንበሽ ገና ኸደጀሰላሙ የልቤን ሳላወጋሽ። የቅርብ ሩቅ ሁኜ ስላንቺ ሰማለሁ። ኸዛ ኸበተክሲያን ወለቴ ምንትዋብ አሉሽ ለኔ ሁሌም ወለቴ ነሽ፡፡ አንድ ቀን ስንኳ ብቅ ስትይ ልቤ ሚተረከከውን ምን ግዝየም አልረሳው። አንድ ቀን ያነን ድንቅ ፊትሽን እሥል ይሆናል። እስተዛው የወፍታው ኻንቺ ጋር ይሁን ብሎ የፍቅራቸውን ምዕራፍ መዝጋት እንዳለበት ለልቡ አስገነዘበ።

አብርሃ የቃረመውን ወሬ ሊነግረው ሲመጣ፣ ጥላዬ መስማት አልፈለገም። “ኸዛው እንኸድና ለሥላሤ ምስጋናዬን ላቅርብ” አለው፣ ወሬውን ሳይጀምር።

“ምናለ፣ እንኸዳ” አለው፣ ግራ የተጋባው አብርሃ።አብርሃ ወደቤቱ ሲሄድ ጥላዬ ቤተክርስቲያኑ ደጅ ላይ ተደፍቶ ምስጋናውን አቀረበ። የተሰበረ ልቡን ሥላሤ እንዲጠግኑለትም ጸሎት
አድርጎ ከዐይኑ ያመለጠውን እንባ ሰው ሳያየው በጋቢው ጠራርጎ ተነሣ።ከመጣ ጊዜ ጀምሮ ሲቀመጥበት የነበረው ዋንዛ ዛፍ ሥር ተቀምጦአካባቢውን ሲቃኝ፣ የቆሎ ተማሪው ግማሹ የለቀመውን ዕንጨት በእቅፉ
ይዞ ወደቤቱ ይሄዳል፣ ሌላው ውሃ ቀድቶ መመለሱ ነው። በየአጥሩ ጥግ መነኮሳትና አረጋውያን ተቀምጠው ዳዊት ይደግማሉ፣ የቁም ጸሐፊው ብራና ላይ ይጽፋል፣ አንዱ ብራና ሲደጉስ ሌላው ቅዱሳት መጻሕፍትን
ያስጌጣል።

ጥላዬ፣ ለሥራቸው በሚሰጡት ትኩረት ተገረመ። እሱም እንደነሱ
ተቀምጦ ሥራውን የሚሠራበትን ቀን ናፈቀ። አለቃ ሔኖክ ትምህርት
እስኪያስጀምሩት ቸኮለ። እዚያው ግቢውን ሲቃኝ ቆይቶ፣ ከሰዐት
በኋላ፣ ወደ እሳቸው ቤት አመራ።
እሳቸው ስላልነበሩ ደጅ ተቀመጠ። ወርቄ በር ላይ ቆማ የሆነ
ያልሆነውን ስትጠይቀውና ሲመልስ ቆይተው፣ ወደ ውስጥ እንደገባች አለቃ ሔኖክ ቅጥር ግቢው ገቡ።

“አምሽተህ ነው?” ብለውት ወደ ውስጥ ገቡ።ቆየት ብለው ወጥተው ወደ ጓሮ እንዲመጣ በእጃቸው አመለከቱት ኩታውን እያስተካከለ ተከተላቸው። ጎጆውጋ ሲደርሱ፣ “ይህቻት
እንግዲህ ማደሪያህ” አሉት።
"እመቤቴ ትስጥልኝ” አላቸው፣ ለጥ ብሎ እጅ ነሥቶ።

አንገቱን ወደ ውስጥ መዘዝ አድርጎ ተመለከተ። ከአንድ አነስተኛ ቁርበት በስተቀር ጎጆዋ ውስጥ ሌላ ምንም ነገር የለም። የአቧራዋ ሽታ ይሰነፍጣል ።

“እዝች ሁነህ ሥራህን ትሠራለህ። የትምርት ግዝየ ሲደርስ እኔ አለሁ።ምግብ ወርቄ ትሰጥኻለች። አንተ ዛዲያ እንጨት ትለቅምላታለህ፣ ውሃ
ትቀዳላታለህ፣ ልብስም ታጥባለህ” አሉት።

“እረ ምን ገዶኝ!”

አለቃ ወደ ቤት ሲመለሱ፣ ቁርበቱ ላይ ጋደም እንዳለ መላ አካላቱ
በሐሳብ ደክሞ ነበርና እንቅልፍ ወሰደው። ምሽት ላይ፣ ወርቄ እራቱን ይዛለት መጣች። ራቱን በልቶ ተኛ።በነጋታው አለቃ ሔኖክ በወርቄ አስጠርተውት ሲገባ እሳቸው መደብ ላይ ተቀምጠዋል። ሰላምታ ሰጥቷቸው በእሳቸው ትይዩ ተቀመጠ።
ወርቄ ቁርስ አቅርባላቸው ከበሉ በኋላ፣ አለቃ ሔኖክ፣ አነስተኛ ብራናና የቀለም ቀንድ ይዘው አብሯቸው ደጅ እንዲወጣ ነገሩት።

“ብራናና ቀለም እኔ ሰጥኻለሁ። ወደፊት ብራና ሆነ ቀለም ራስህ
ታዘጋጃለህ። ቀለም አቀማመም አሳይሀለሁ። ንድፍም አሳይህና በዚያ መሠረት ኸርኩሳኑ መኻል ምትፈልገውን ሠርተህ ታመጣልኛለኸ አሉት።

እጅ ነሥቶ ትኩረቱን እጃቸው ላይ ያለው ብራና ላይ አደረገ።
ቀስ ብለው ንድፍ እንዴት እንደሚሠራና ቀለም እንዴት እንደሚቀባ አሳዩት።
“ለነገሩ ንድፍ አይቸግርህም። በአክርማ ስትሠራ ቆይተህ የለ?”
አሉት፣ እየሳቁ።
ዐይኑን ከብራናውና ንድፉን ከሚሠሩበት የቀርከሀ ስንጥር ላይ
ሳያነሳ በአዎንታ ራሱን ነቀነቀ።

ትምህርቱን ጨርሰው እሳቸው ወደ ውስጥ ሲገቡ፣ እሱ ወደ ቤቱ
ሄደ። ጋቢውን ቁርበቱ ላይ ወርውሮ ደጅ ድንጋይ ላይ ተቀምጦ፣ለመጀመሪያ ጊዜ ሲመኝ የኖረው ብራና እጁ በመግባቱ ሊስመው ቃጣው።

ሕይወቱ ዐዲስ ምዕራፍ የያዘ መሰለው።ሥዕሉን በምን እንደሚጀምር አወጣ አወረደ... እባብ? ሳጥናኤል? ቁራ? በመጨረሻም ስለምን ሳጥናኤኔልን አልሰራም አለ፣ ለራሱ።አለቃ ሔኖክ ባሳዩት መሠረት ንድፍ ሞከረ፤ ተንጋደደበት። ብራናውን
ያበላሽ ስለመሰለው ደነገጠ። ሆኖም መሣሉን ቀጠለ። አለቅጥ ረጀም፣ግራና ቀኝ አስፈሪ ቀንዶች ያለው፣ ጆሮዎቹ በጣም ትልልቅና ጭራ ያለው ፍጡር ሣለ። ቤቱ ደጃፍ ላይ ተቀምጦ፣ ብራናውን ደጋግሞ እየተመለከተ ስቆ እንደማያውቀው ሳቀ። በነጋታው ፈራ ተባ እያለ አለቃ ሔኖክጋ ሲሄድ ወርቄ፣ “ኣፍህን እንድትሽር ልጠራህ ስል መጣህ” አለችው።

“ለመብልማ እስትትጠራ አትጠብቅ። ቤትህ እኮ ነው” አሉት፣ አለቃ ሔኖክ።

ቁርስ አድርገው ከጨረሱ በኋላ፣ “እስቲ ምን ሠራህ?” አሉት።

ብራናውን ብድግ ብሎ ሲያቀብላቸው፣ ቀረብ፣ ራቅ አድርገው ተመለከቱትና ሳቁ። “ሳጥናኤል... ማለፊያ ነው። ንድፉም መልካም ነው። ተሰጥኦ እንዳለህ ያስታውቃል” አሉት።

“ንድፉ ተንጋደደብኝ እንጂ።”

ርኩሳንን ከሀዲያንን፣ አጋንንትንና ክፉዎችን ስትሥል ንድፉ ቢንጋደድ ምንም አዶለም። ባሕሪያቸው ነው፤ መንጋደድ ይስማማቸዋል። ላንተ ግን ዋናው እጅ ማፍታታትህ ነው። ወደፊት ቅዱሳንን፣ መላዕክትንና ሌሎችን ስትሥል ግን ንድፍ ማንሻሽፍ
አይፈቀድም። በል በርታ” ብለው ብራናውን መልሰው ሰጡት።

እጅ ነሥቶ ወጣ።

በሚቀጥሉት ቀናት፣ እሳቸው በነገሩት መሠረት ጥቁር ቀለም ከተለያዩ ዕጽዋት ቀምሞ ሥዕል መሣሉን ተያያዘው። እንደሱ ቢሆን፣ ርኩሳንን ብቻ ሳይሆን የፈለገውን ቢሰራ በመረጠ። ብዙውን ጊዜ የምንትዋብ
መልክ ፊቱ ላይ ድቅን ይላል። እንደበፊቱ እንስሳውን ቤቶቹን ሁሉ
መሣል ይፈልጋል። አንዳንዴ የፈለገውን የሚሥልበት የቤታቸው ጓሮ ይናፍቀዋል።

ሥዕል በማይሥልበት፣ ለወርቄ ውሃ በማይቀዳበት፣ ዕንጨት
በማይለቅምበትና የአለቃ ሔኖክን ልብስ በማያጥብበት ጊዜ፣ ከአብርሃ ጋር ጃን ተከል እየሄደ ወሬ ይሰማል። ጃን ተከል ብቅ ማለት እሱስ ሆኖበታል። ቤተመንግሥት ግብር ሲጣል፣ አብርሃ ምግብ ብቻ ሳይሆን
ስለ ምንትዋብ ወሬ ይዞለት ይመጣል ።

በትምህርቱ እየጎበዘ ሲመጣ፣ አለቃ ሔኖክ በሥራው ቢደሰቱም፣
“መልካም ነው፣ በርታ” ከማለት በስተቀር ብዙ ስለማያብራሩ ጥቂት ቅር ይሰኛል፣ ቢያሞጋግሱት ይመርጣል። የሠራውን ሲመለከቱ፣ ፊታቸው
ላይ የሚንፀባረቀውን አድናቆት ለምን በቃላት እንደማይገልጹለት
ይገርመዋል።

አንድ ቀን አስደሰቱት። ግቢው ውስጥ ተቀምጠዋል። እንዴትና
የት እንደዋለ ከጠየቁት በኋላ፣ “ጥላዬ፣ ሥዕል ኸዠመርህ ወራት
አልፈውሀል። እጅህም ጥሩ ተፍታቷል። እንደነገርሁህ ጥቂት ቆይተህ ቄሶችን፣ መሪጌታዎችን፣ ሊቀጠበብቶችን ቤተክስቲያን አካባቢ ያሉ ሰዎችን መሣል ትዝምራለህ” አሉት።

ደስ ተሰኘ።
👍15😱1
“በርታ እንግዲህ። እስታሁን ጥሩ እየሠራህ ነው። ወደፊት ደሞ
የበለጠ እየተፈተንህ ትኸዳለህ።”
ማንን እንደሚሥል ሲያስብ ከረመ።.....
፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡ ፡
በእነዚያ ወራት፣ “እቴጌ አርግዘዋል መሰል ጠዋት ጠዋት ወደላይ
ይላቸዋል” የሚል ወሬ ቤተመንግሥቱን አልፎ ጃን ተከል ሲመጣ እሱምጋ ደረሰ። የምንትዋብ እርግዝና የሁሉ ጉዳይ በመሆኑ ተገረመ።

አንድ ቀን፣ ጃን ተከል ከምንጊዜውም የበለጠ ተጣቧል። እሱና አብርሃ ገና መድረሳቸው ነው። ሰዉ በቡድን በቡድን ሆኖ ይወያያል፣ ይከራከራል፣ ይሟገታል። ጥላዬ አንዱጋ ተጠግቶ ሲያዳምጥ ወሬው ዛሬም ስለምንትዋብ እርግዝና ነው፡፡

“እቴጌይቱ ወንድ ኻልወለዱ ንጉሡ እንዴት አርገው ነው አልጋ
ወራሽ ሚያገኙ?”
ፊት የወለዷትም ሴት ናት አለ።”

“እቴጌም ሴት ኸወለዱ ጉድ ነው በለኛ!”

“ኸጉድም ጉድ ነው እንጂ።”

ጥላዬ አላስቻለውም። ጣልቃ ገባና፣ “ኸምኑ ላይ ነው ጉዱ?” አለ።
“ኧረገኝ ምን ያለ ዥል ነው በሉ? የተዣዣለ። ሴት መንገሥ
እንደማትችል አያውቅም ሁኖ ነው? አይበለውና እቴጌ ሴት ቢወልዱ እንዴት ሁኖ ነው ንጉሡ አልጋ ወራሽ ሚኖራቸው? በል እስቲ ንገረኝ?”
ጥላዬ፣ ሊቀጥለው የማይችልበት ሙግት ሆነበትና ዝም አለ።
አብርሃን በዐይኑ ፈልጎ ሲያገኘው አብርሃ የአንገቱ ስሮች እስኪገታተሩ ድረስ ከሁለት ሰዎች ጋር ይከራከራል። ጥቂት ጠብቆት ወደቤቱ ሄደ።

ቤት ሲደርስ፣ አለቃ ሔኖክ ከሰዐት በኋላ እንደሚያደርጉት ጥላ ስር
ተቀምጠው ቀለም ይቀምማሉ። አጠገባቸው ሄዶ ተቀመጠ።

“የት ቆይተህ ነው?” አሉት
“ከአብርሃ ጋር ጃን ተከል ወርደን የሰዉ ክርክር ለብቻው
አላቸው።

“ስለምን ነው ሚከራከሩ?”

“ስለ እቴጌ...” ምንትዋብ ይበላት ወለቴ ቸገረው። ገና ምንትዋብ
የሚለውን ስም አልተለማመደውም። “እቴጌዋ አርግዘዋልና ወንድ በሆነ
እያለ ሰዉ ይነታረካል።”

“መቸም ውነት ነው። ለእቴጌም ሆነ ለንጉሡ ወንድ መሆኑ ይጠቅማል።በዝኸ ግዝየ እቴጌስ ቢሆኑ ተኝተው ያድሩ መሰለህ? ቤተመንግሥት ውስጥ ያለ ወሬ ስንኳ አያስተኛቸውም። ወንድ ቢሆንላቸው ንጉሡን የሳቸው ደጋፊ የሆኑትን መኳንንት ጭምር ያስደስታሉ። እሳቸውም
ልባቸው ያርፋል።”

“ፈርዶባቸዋላ!”

“እዝጊሃር ይርዳቸው። በዝኸ ላይ ኸቋራ ናቸው።”

“ኸቋራ ቢሆኑ ምን ሞገድ አለው?”

“አየ ጥላዬ! አለው እንጂ። በአንድ በኩል መኳንንቱ የቋራ ደም
ያለው አልጋው ላይ እንዲወጣ አይፈልጉም። ቋራ እንደ ጐንደር
ማዶል። ባላገር ነው ብለው ያስባሉ። በሌላ በኩል ደሞ እወህኒ አምባ ስንቱ የነጋሢ ዘር መሰለህ አሰፍስፎ ሚወለደው ወንድ ይሁን ሴት ሚጠባበቀው። ወንድ ኸተወለደ የመንገሥ ዕድላችን ይዘገይብናል
አለያም ያመልጠናል ብለው ይሰጋሉ። ሴት የሆነች እንደሁ እነሱም ይደሰታሉ፣ ከንጉሡ ጋር ጠብ ያላቸው መኳንንትም የልባቸው ይደርሳል። ንጉሡም ቢሆኑ ዳግም ሴት ኸተወለደችላቸው ያዝናሉ።
አየህ ነገሥታቱ አልጋቸውን አሳልፈው መስጠት ስለማይፈልጉ ወንድ ልዥ ለማግኘት ሲሉ ዕቁባት ይይዛሉ። አሁን አጤ ቴዎፍሎስ...
የታላቁ ኢያሱ ወንድም፣ የጃንሆይ አጎት መሆናቸው ነው... ከሕግ
ባለቤታቸው ኸእቴጌ ወለተጽዮን ጠንተው ሲኖሩ እቴጌዋ መካን ነበሩና አልጋ ሚወርስ ልዥ አልነበራቸውም። ስለዝኸ የነጋሲ ዘር የሌላቸው የአጤ ቴዎፍሎስ እንደራሴ የነበሩት ዮስጦስ ነገሡ። አሁንም ጃንሆይ ቢሞቱ ስንኳ አልጋቸውን ሚወርስ ልዥ የለም። ለዝኸ ነው ያ ሁሉ ክርክር።”

“እቴጌ ሴት ኸወለዱ ጉድ ነው ቢሉ ጉዱ ምኑ ላይ ነው ብል አንዱ ዥል የተዣዣለ ብሎ ሰደበኝ” አላቸው፣ እየሳቀ።

አለቃ ሔኖክ እንባቸው ጠብ እስኪል ሳቁና፣ “እንግዲህ ለእቴጌ
እንጸልይላቸዋለን” አሉት።
ኧረ አጥብቄ ጸልይላታለሁ አለ፣ ለራሱ።......

ይቀጥላል
👍15
አትሮኖስ pinned «#ምንትዋብ ፡ ፡ #ክፍል_አስራ_አራት ፡ ፡ #ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ ...ጃን ተከል ከወትሮው የበለጠ ሰው ተሰብስቦበታል። ወሬው ሁሉ ስለ ቅዳሜው ግብርና ስለ ምንትዋብ ውበት ነው። ቅዳሜ ዕለት ኣብርሃ ቤተመንግሥት በር ላይ የድኃ ተራ እስኪደርስ ጠብቆ ግብር ተካፍሎ ነበርና በአኮፋዳው ከየዓይነቱ ምግብ ጠቅጥቆ መጥቶ ጥላዬን እንዲበላ ሲጋብዘው አልበላም ብሎታል። አብርሃ ምንትዋብን ባያያትም፣ ስለግብሩ…»
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሰላሳ_አንድ


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ

...«አምጡት እንግዲው!» አላች ታፈሡ በልሁና መርዕድን በፈገግታ አይን እያየቻቸው።.

መርዕድ አልዘገየም፤ የመቃሚያውን ቦታ በአዲስ መልክ አበጃጀው ጫቱን ከጋዳ ውስጥ አወጣ። ያ ቤት እንደገና ነፍስ ዘራ። የጫቱ መጀመር በተለይ በታፈሡና በሔዋን እናት መካከል ተጨማሪ ውይይት እንዲፈጠር ምክንያት ሆነ።
«በልሁ» ስትል ታፈሡ መጀመሪያ ጠራችው፡፡
«አቤት»
«የሒዩ እናት ትናንት ሸዌዬ ቤት እንዳደሩ ነገሩኝ፡፡ ነገር ግን ደስ ያላቸው አልመስለኝም፡፡» አለች በተለይ የሔዋንን እናት አየት እያደረገች::

«ከፋዎት እንዴ እማማ?» ሲል ጠየቃቸው በልሁ፡፡ቢከፋኝስ የት እደርሳለሁ ብለህ የኔ ልጅ አሉ የሔዋን እናት ጉንበሰ ብለው መሬት መሬት እያዩ።
ቀድሞ ነገር በልጅዎ ቤት ለምን ይከፋዎታል? አለ በልሁ አሁንም፡፡
«ምኑን አወቅት ብለህ የኔ ልጅ! እንግዲህ እያደር ሳውቀው ይገባኝ እንደሆነ እንጂ እስታሁንስ ነገሩ ሁሉ ግራ ግብት ነው ያለኝ» አሉ የሔዋን እናት::
ታፈሡ ወደ ሔዋን አየት እያረገች ሔዩ! ለእማማ ሁሉንም ነገር
ልነግራቸው ነው ከፋሽስት አልከፋሽ የራስሽ ጉዳይ» አለቻት በመቀለድ ዓይነት
ሔዋን አንገቷን ወደ መሬት ቀበረች፡፡ እናቷ ሳይቀሩ በልሁ፣ መርዕድና ታፈሡም ያዩዋት ጀምር። በዚህ ግዜ እናቷ፣
ነውር የሆነ ነገር ሰራሽ እንዴ እመ'ዩ?» ሲሉ ጠየቋት፡፡
የእርስዎ ልጄ ነወር ልትሰራ አልተፈጠረችም::» አለች ታፈሡ እንደገና ወደ በልሁና መርዕድ ዞር ብላ «ያ ሲያስጨንቀን የነበረ ሸዋዬ ስለ ሔዋን ለወላጆቿ
የፃፈችው ደብዳቤ እኮ አልተላከልንም» አሉ አለቻቸው ሁለቱንም አየት አየት
እያረገቻቸው
«ሙት በይኝ» አለ በልሁ።
አያችሁ! ሔዩም ስትጨነቅ፣ አስቻለውም እኛም ስንታመስ የኖርነው እንዲሁ በከንቱ ኖሯል» አለችና የተፃፈው ደብዳቤ ይዘት ምን እንደነበረ ዘርዘር አድርጋ ለሔዋን እናት አሰረዳቻቸው፡፡ ሸዋዬ ያን ደብዳቤ ሔዋንን ለማስፈራራትና ለማስደንገጥ እንጂ ልትልከው እስባ እንዳልነበር እንደ አዲስ ታሰባቸው፡፡
የሔዋን እናት የደብዳቤውን ይዘት ከታፈሡ ገለፃ ከተረዱ በኋላ “ይህን ነገር እሙዬ ፈፅማው ነው ወይስ ...» ብለው ታፈሡም ሔዋንንም ሲመለከቱ ታፈሡ ራሷ ቀጠለች::
«አዩ እማማ! መቸም ሔዩም ሽዋዬም ልጆችዎ ናቸው። በእርስዎ ፊት አንዷን ወግነን ሌላዋን ብናማ ትዝብት እንደሆነ እንጂ ሌላ እንደማናተርፍ
እናውቃለን፡፡ ግን ደግሞ እውነቱን ግልጥልጥ አድርገን ልንነግርዎት እንፈልጋለን።አለቻቸው አንድ የጫት እግር ይዛ ወዝወዝ ወዝወዝ እያደረገች፡፡
«በጄ» አሏት የሔዋን እናት ለነገሩ እየጓጉ።
«ሔዩና ሽዋዬ በሚያጣላ ነገር ተጣልተው ለማስታረቅ ብዙ ጥረን ነገር ግን በሸዋዬ እምቢተኝነት ሳይሳካልን ቀረ፡፡
«ምን አጣላቸው የኔ ልጅ?»
ታፈሡ ነገሩን ከሥሩ ጀመረችላቸው በቅድሚያ እሷና ሸዋዪ የትና እንዴት እንደሚተዋወቁ ሸዋዬ ከያቤሎ
ወደ ዲላ ስትመጣ ያደረገችላትን
አቀባበለ፤ ቀጥላም የእስቻለውን ምንነትና ማንነት፤ ከእሷ ጋር የነበረውን ግንኝነትም እንዲሁ ገለፀችላቸው፡፡ በመጨረሻም የአስቻለውንና የሔዋንን ጉዳዩ
ከአጀማመሩ እስከ የወደፋት አላማቸው ድረስ አስረዳቻቸው
ለዚህ ነገር የሸዋዬ አቋም ምን ይመስል እንደነበር ችግሩን ለመፍታት የተደረገውንና ሊደርግ
የነበረውን ጥረት ሁሉ ዘረዘረቾላቸው።
የሔዋን እናት በነገሩ መመሰጣቸው የተነሳ በወሬው መሀል ቢጠሯቸው
እንኳ "ወያ" የሚሉ አይመስሉም፡። እንዲያውም እንባቸው እየመጣ በለበሱት ነጠላ ዓይናቸውን ጨመቅ ያደርጋሉ፡፡ ሔዋንንም ዞር እያሉ ስሜቷን ሲሰልሉ እንባዋ
በጉንጯ ላይ ሲፈስ ያያሉ በዚያው ልክ ሆዳቸው ይንቦጫቦጫል የእሳቸው ሁኔታ የሁሉንም ቀልብ ስቦ ሁሉም በትካዜ አስተያየት ያዩአቸዋል፡፡
ታፈሡ አሁንም የሔዋንና የሸዋዬን ለየብቻ የመኖር ምክንያት ልትጠቁማቸው ፈልጋ ሸዋዬ ሔዋንና አስቻለውን ለመለያየት ያደረገችውን ጥረትና ሔዋንም በማትፈልገው ሰው ልታስደፍራት መሞከሯን ጭምር ነገረቻቸው።
የሔዋን እናት ነገሩ ሁሉ ግርም አላቸውና «እንዴት ነው ይኸ ነገር
እሙዬ» ሲሉ በተላይ ሔዋንን እያዩ ጠየቋት፡፡ ምናልባት እሷም በሆዷ ውስጥ ያለ ነገር ካለ ብለው ብትነግራቸው ፈለጉ።
«ሔዋን ፤ ኢይዞሽ ንገሪያቸው!» አለች ታፈሡ በልጃቸው አንደበት ቢሰሙ የበለጠ ላያምኑ እንደሚችሉ በመገመት።
ሔዋን ግን አልቻለችም። ለቅሶ ቀደማትና በእናቷ “ጭን ላይ ድፍት በማለት ትንሰቀሰቅ ጀመር፡፡ እናቷም ታፈሡም ቢያባብሏት ዝም ልትል አልቻለችም በመሀል በልሁ ተቆጣት።
“እንቺ ሔዋን» አለና ከመቀመጫው ብድግ አለ፡፡ «ቀና ብለሽ ቁጭ በይ።ለምን የእናትሽን ሆድ ታባቢያለሽ?» አለና አንገቷን ደገፍ አድርጐ ቀና አደረጋት፡፡
«እናትሽ የጠየቁሽን መልሽላቸው።» አላት እንደገና።

«አ- አንቺ ን- ንገሪያት ታፈሡዪ!» አለች ሔዋን ድምጿ እየተቆራረጠ፡፡ታፈሡ ቀጠለች:: በመሀል ደሞ አንድ ችግር ተፈጠረብን እማማ። ይህ
እስቻለው ያልከዎት ወንድማችን ሳያሰበው በዘመቻ ስም በግዳጅ ወደ ኤርትራ መሄድ ግድ ሆነበት።
ይህም አጋጣሚ የተፈጠረው በሸዋዬ አማካኝነት ልጁንና
ሔዋንን ለመነጣጠል የተዶለተ ሴራ መስሉ ታየንና ሔዋን ያለ ፍላጎቷ ከመደፈሯ በፊት ማሸሽ ፈለግን። ልጁም ደሞዙን ለእሷ መተዳደርያ እንዲሆን አድርጎ ስለነበረ ከሽዋዬ ቤት ወጥታ እዚህ ቤት እንድትኖር አደረግን፡፡ በቃ ሔዋን ከሸዋዬ ቤት የወጣችብት ምስጢሩ ይህ ነው የኔ እናት» አለቻቸውና ምላሻቸውን በመጠበቅ ዓይኗን በዓይኖቻቸው ላይ ስክት አደረገቻቸው።
ለልጁ መዝመት መዘዘኛዋ ያቸው የእኔ ልጅ ናት በይኛ» አሉና የሔዋን እናት ታፈሡን ያዩዋት ጀመር።
«እውነተኛውን ነገር እግዜር ይወቅ እማማ በኛ በኩል ግን እንደዚያ
ገመትን፡፡» አለችና ታፈሡ እጆቿን ጨብጣ አገጯን በማስደገፍ የሔዋንን እናት እየተመለከተች «አስቻለው ከመስሪያ ቤት አለቃው ጋር አይስማማም ነበር። ሽዋዬ
ደግሞ ከዚያ ሰው ጥብቅ የሆነ ግንኙነት ፈጠረች፡፡ እኛም በዚህ ጉዳይ የተነጋገሩበትና በጋራ የፈጠሩት መላ ሊሆን እንደሚችል ጠረጠር።አለቻቸው
የሔዋን እናት ያላሰቡት ስሜት ተፈጠረባቸው፡፡ በግራ እጅ መዳፋቸው ጉንጫቸውን ደገፍ አድርገው «እየየ እኔ! እየየ እኔ! ..» በማለት የተሰማቸውን ሃዘን ሲገልፁ እንባቸውም ከአይናቸው ላይ ድንቡቅ ብሎ ወረደ በዚህ ጊዜ በልሁ ብድግ ብሎ ወደ ጓዳ ገባና ቀድሞ የአስቻለው አሁን ደግሞ የሔዋን ከሆነው አልጋ የራስጌ ኮመዲኖ ላይ ሁለት ትላልቅ ፎቶግራፎች ይዞ ተመለሰ አንዱ አስቻለው ለብቻው የተነሳው ሌላው ደግሞ ወደ ኤርትራ ከመሄዱ አንድ ቀን በፊት ከሔዋን ጋር በመሆን በቁም የተነሱት ነበር። ሁለቱንም ፎቶግራፎች ለሔዋን እናት እየሰጠ እዩት እማማ! «ልጁም ይህ ነበር» አላቸው።
የሔዋን እናት ፎቶግራፎቹን በጭናቸው ላይ አስቀምጠው ልክ እንደ ፊት መስታወት እያዩ በቀኝ እጃቸው ቡጢ ደረታቸውን ደስቅ ደሰቅ እያደረጉ እ - እ እ ካሉ በኋላ ዓይኔ ይፍለስ! ዓይኔ ይፍስስ! ዓይኔ ይፍሰስ» አሉና «ምነው ይኽን ጉድ ሳነልሰማ ሞቼ አርፊው ቢሆን!» በማለት ከሁንም ዓይንና አፍንጫቸውን በነጠላቸው ይጠራቸው ጀመር።
👍91
«አይቀየሙኝኛ» አለ በልሁ ሔዋንና ሽዋዬ ከአንድ እናት ማህፀን የወጡ
አይመስለኝም እማማ ቅር ይልዎት ይሆን?» ሲል ጠየቃቸው፡፡
«የእናት ሆድ ዥንጉርጉር የተባለው ስለዚህ አይደል የኔ ልጅ! አንተም
በኔም ሆድ ብዙ አለ፡፡» አሉና ድንገት በሀሳብና በትካዜ ውስጥ ጭልጥ ብለው ገቡ።
የሸዋዬን የልጅነት አስተዳደግ እያስታወሱ ነው፡፡ ሽዋዬ በህፃንነቷ ገና በእቅፋቸው ውስጥ ሆና ጡታቸውን ጠብታ ጠብታ ስትጠግብ እንዴት አድርጋ ትነክሳቸው እንደነበር ትዝ አላቸው፡፡ ጠንክር ብላ ወደ ውጭ
መውጣት ስትጀምር ደግሞ
ከጎረቤት ልጆች ጋር ባለመስማማት ወይ አልቅሳ አለያም አስለቅሳ በመመለስ
የምታመጣባቸውን ስሞታ ሁሉ አስታወሱ። በቤት ውስጥ ደግሞ አጥፊ አውዳሚ፣ ምንም ነገር፣ የትም ቦታ ቢደበቅ የማያመልጣት ሰርሳሪ በዚያ ላይ ደግሞ ሰባቂ፣ የእናቷን ሚስጢር ለአባቷ፣ የአባቷን ደግሞ ለእናቷ እየነገረች
የምታሳጣቸው ሰላም እንኳ እልቀራቸውም፡፡ “ይቺ መሄጃዋ የማይታወቅ መዘዘኛ እያሉ ገና በልጅነቷ ይማረሩባት የነበረው ሁሉ ትዝ አላቸው።
ለአፍታ ያህል ፀጥታ ሰፈነና ከቆይታ በኋላ ግን የፀጥታውን ድባብ ራሳቸው' የሔዋን እናት ቀድመው ሰበሩት፡፡ ለመሆኑ ልጁ መቼ ይሆን የሚመለሰው?» ሲሉ ጠየቋቸው።
ታፈሡና በልሁ ድንገት ድንግጥ ድንግጥ አሉና እርስ በርስ ተያዩ።
መርዕድ ግን ከእነሱ በባሰ ሁኔታ ደንግጦ ውጭ ውጭ ያይ ጀመር፡፡
«ግራ ገብቶናል እማማ::» አለች ታፈሡ እሷም ብትሆን ቀጥላ የምትለው ነገር አስፈርቷት መሬት መሬት እያየች፡፡

«እንዴት የኔ ልጅ?»
የሄደው ለስድስት ወር ተብሎ ነበር፤ አሁን ግን ይኸው ዓመት ሊሞላው ነው። ግን እልም ብሎ ጠፍቶብን በሀሳብ ላይ ነው ያለነው::» አለችና ወደ በልሁ
ዞር ብላ ምናልባት ግን ሰሞኑን አንድ ነገር ስምተናልና የተስፋ ጭላንጭል ነው ብለን ገምተናል ብላ በልሁን 'ተናገር' በሚል ስሜት
በዓይኗ ጠቀስ አደረገቻቸው ተግባብተዋልና በልሁ ቀጠለ።
«ይህን ነገር ለሔዋንም ልንነግራት ነበር ዛሬ የተሰበሰብነው ሲል ጀመረ። «ደሞዙን ከመስሪያ ቤቱ እያመጣሁ ለሔዋን የምሰጣት እኔ ነበርኩ። ከጥቂት ቀናት በፊት ሄጄ ስጠይቅ ግን ደሞዝ ተቋርጧል የሚል ወሬ ሰማሁ፡፡» አለና ቀና ብሎ ሔዋንና እናቷን እየተመለከተ
ያን ቀደም ሲል ከእነታፈሡ ጋር ሆነው የፈጠሩትን ሔዋንን የማረጋጊያ ዘዴ መተረክ ጀመረ። አስቻለው በምጽዋ በኩል ወደ ውጭ ሄዶ ሊሆን እንደሚችል፤ ጀርመን ወይም ጣሊያን ሀገር ገብቶ ሊሆን እንደሚችል
ደብዳቢው በቅርቡ ሊመጣ እንደሚችል …ወዘተ። በልሁ በዚህ ዙሪያ ብዙ ብዙ ተናገረ።
በዚህ ትረካ ምናልባት የሔዋን እናት ተታልለው ሊሆን ይችላል፣ ሔዋን ግን የአስቻለውን ደሞዝ መቋረጥ ስትሰማ አይኗቿ ወደ ዳር ወተው ተጎለጎሉ ትን ትንፋሿም በርከት በርከት ፈጠን ፈጠን ማለት ጀመረ:: ታፈሱና በልሁ ስሜቷ ገብቷቸው በፍርሃት አስተያየት ሲመለከቷት ሔዋን ድንገት ተናገረች.
«ምን እያልክ ነወ በልሁ?» ስትል ጠየቀችው፡፡
«አትጠራጠሪ ሔዋን፣ ይሄ ነገር ለበጉ ነው፡» አላት ምላሽ የምትሰጥ ከሆነ ብሎ አይን አይኗን እያየ።
የሔዋን ሁኔታ የበለጠ እያስፈራራ ሄደ። ዓይኖቿ እንደፈጠጡ ቀሩ፡፡
በታፈሡና በበልሁ እንዲሁም በመርዕድ ላይ አከታትላ ታንከራትታቸው ጀመር።ወዲያው ደግሞ በረጅሙ ተነፈሰችና ወደ መሬት አጎነበሰች 'ኤርትራ የሄደ ይመለሳል ብለሽ.." የሚለው የበድሉ አነጋገርም ድንገት ፊቷ ላይ ድቅን አለባት፡፡
የሔዋን እናት ልጃቸውና ጎደኞቿ የተግባቡት ነገር እንዳለ ገባቸው
«ለመሆኑ እናቱ በሕይወት አሉ?» ሲሉ ጠየቁ፡፡
«እናትም አባትም የለውም፣ ሁለቱም ሞተውበታል፡፡» አለች ታፈሡ፡፡
የሔዋን እናት ከንፈራቸውን መጥጠው ዝም አሉ፡፡ አገጫቸውን በመደገፍ ወደ መሬት አጎነበሱ፡፡ ለአፍታ ያህል እሁንም ፀጥታ ሰፈነ። በመሀል ታፈሡ አንድ ነገር ትዝ አላት፡፡ ወዲያውም ማደናገሪያ ይሆናል ብላ በማሰብ ሳይሆን አይቅርም በልሁና መርዕድ የገዙትን ሥጋ ከጓዳ ወደ ሳሎን አመጣችና የእራት ወጥ
ለመስራት መከታተፍ ጀመረች። ፀጥታው ግን አሁንም ቀጠለ፡፡
«ተጫወቱ እማማት» አለ በልሁ ከብዙ ቆይታ በኋላ፡፡
«ልጆቼ» ሲሉ የሔዋን እናት ሁሉንም በአንዴ ጠሯቸው::
«አቤት እማማ?» አለች ታፈሡ ቀድማ፡፡ ግን ሁሉም ቀና ቀና ብለው ያይዋቸው ጀመር
«ታዲያ የእሙዬን ነገር እንዴት ባደርግ ይሻላል?» ሲሉ ጠየቁ፡፡
«እንዴት?” እላቸው በልሁ።
«የልጁ መምጫ ቀን አልታወቀም አላችሁ፡፡ በያ ላይ ደሞዙ ተቋረጠ ነው የምትሉኝ:፡ ታዲያ ወይ ይዣት ልሂድ?» ሲሉ ፈራ ተባ እያሉ ጠየቁ፡፡
ሁሉም ደነገጡና ዝም ዝም አሉ፡፡ ግን ደግሞ እርስ በእርስ ተያዩ።
«አይሻልም ብላችሁ ነው ልጆቼ? ወይስ ቅር ይላችሁ ይሆን?»
ሔዋን ስትል ታፈሠ ጠራቻት። ከመደንገጧ የተነሳ እንጂ ወይ ብትላት ቀጥላ የምትናግሪውን ነገር ታፈሡ አላዘጋጀችም።
«እሄዳለሁ» አለች ሔዋን ድንገት ሳትታስብ፡፡
«እ» አለ በልሁም ድንገጥ ብሎ።
«አዎ ከእማዬ ጋር ወደ ሃገሬን እሄዳለሁ።»አለች ሔዋን አሁንም ድርቅ ባለ ስሜትና ማጠንከር ባለ አነጋገር።አይኖቿ ግን አሁንም እንደተጎለጎሉ ናቸው። አንዳች ከብር ውስጧን ያናወጠባት ትመስላለች በዚህ ጊዜ ያልታሰበ ድምጽ፤ ባልታሰበ አኳኋን ካልታሰበ ሰው ተሰማ
ትርፌ እኔስ እታለምዬ ብላ ልክ እንደ ልጅነቷ ግንባሯን በክንዷ ሸፍና እይይይ…" ብላ አለቀሰች፡፡
ተይ እንጂ! ምን ነካሽ? እኛ እያለን! እኛ እያለን!» በማለት ታፈሡም በልሁም መርእድም አከታትለው ተንጫጩባት
እሷ ግን ዝም አላለችም፡፡ እንዲያውም በለቅሶዋ መሀል ልክ ቤት ውስጥ እንደምትጠሪው አይነት “ጋሽ አስቻለው…!» ስትል በርቀትና በጩኸት ድምጽ ተጣራች። አስቻለው ወደ አስመራ፣ ሔዋን ወደ ክብረ መንግስት
ተነጣጥለው ሲሄዱ እሷ ጭር ባለ በረሃ ውስጥ ብቻዋን የቀረች መሰላት። ሆዷም ባባና ስቅስቅ ብላ አለቀሰች።
«ታፈሡዬ አለች ሔዋን በመሀል
በዚያው ድርቅ ባለ ስሜት ውስጥ ሆና።
«ወይ የኔ ቆንጆ»
ሔዋን ግን ጥሪዋን ቀጠለች፡፡ «በልሀዬ! መርዕድ!» አለች በማከታተል።
«ወይ! አቤት» አሏት ሁለቱም፡፡
ለእስቹ ፀልዩለት። ትርፍዬን ደግሞ አደራ!!» አለቻቸው።......

💫ይቀጥላል💫
👍121
#ሞገሰኛ_ኑሮ

ተስፋ ያልቆረጠ
ወድቆ የተነሳ
በሕይወት መዝገብ ላይ
ታሪኩ ይፃፋል
ባለ ድል ነውና
የሄደበት ሁሉ
አሻራው ይሰፋል
እንኳንስ በገሃድ
በጥላው ይገዝፋል!!!

🔘ሰለሞን ሳህለ🔘
👍94
#የተልባ_ስፍር

ሕልምና ምኞትሽን
ሃፍረት ሳይለጉምሽ አስበሽ ነገርሽው
“አንጉደል እንሙላ
እሺ በለኝና ያንተ ልሁን” አልሽው
ላንች ግልግል ነው
ሃቁን ተናግረሻል ለ'ሱ እንጂ ሰቀቀን
ቃል ያጠፈ ዝናብ
ሞልቶ ያፈሰሰው በርሚል ሳይደቀን
ሂያጇም ብላው ነበር
እሺታውን ሳትገድል ከዕለታት ባንዱ ቀን!

🔘ሰለሞን ሳህለ🔘
12👍5
#ምንትዋብ


#ክፍል_አስራ_አምስት


#ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ

...ጥላዬ፣ ከአለቃ ሔኖክ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እየመሠረተ ሲመጣ፣ብዙ ጊዜ አብሯቸው መቀመጥና መጫወት ሥዕል ከመሣል ቀጥሎ የሚያስደስተው ነገር ሆነ። ወደፊትም እንደሳቸው ጥበበኛ መሆን አበክሮ ተመኘ። ላደረጉለት ሁሉ ሲያመሰግናቸው ቢውል አላጠግበው አለ።

“አለቃ ላረጉልኝ ሁሉ እመቤቴ ምላሹን ትስጥዎ” አላቸው፣ አንድ
ቀን እንደወትሮዋቸው ግቢ ውስጥ ተቀምጠው ሲያወሩ።

“እኔኮ ማስተምረው ኸተማሪዎቸ ጥቅም አገኛለሁ ብየ ማዶል። ልክ
መምህሬ የነበሩት አለቃ ወልደሰንበት ደከመኝ ሳይሉ፣ ሚያውቁትን ሁሌ ሳይሸሽጉ እንዳሳተማሩኝ ሁሉ ተማሮቸን ማስተማር ፈልጋለሁ።ዋጋየ እናንተ ተማሮቸ ጥሩ ተምራችሁ ለጌታችን ያላችሁን እምነት፣ ክብርና ፍቅር በሥራችሁ ስታሳዩ፣ የመጻሕፍትን ምሥጢር አንብባችሁና ተረድታችሁ በሥዕል ስትገልጡ ነው። ሥዕል ዋናው ዓላማው ቤተስኪያንን ማስጌጥ ማዶል። ሥዕል እኮ ታሪክ ነው ሚነግር፤
ሥዕሉ ራሱ እኮ ወንጌል ነው። ምእመኑ የመጻሕፍቱን ምሥጢር
አውያቁም፣ አያነቡም፡ አይረዱም። ስለዝኸ የእናንተ ሥራ የመጻሕፍቱን ምሥጢር... ወንጌሉን በሥዕል እንዲረዱና መንፈሳዊነት፣ አክብሮትና
ፍራት በልባቸው እንዲያድር ማረግ ነው። ባለፈው እንደነገርኩህ ካህናቱ አምስቱን አዕማደ ምሥጢር በንባብ በሐተታ ይማራሉ።ምእመኑ ግን በሥዕል ነው ሚማር። ቀዳሚው ምሥጢረ ሥጋዌ ነው፣ኸገብርኤል ብሥራት ትጀምራለኽ። ገብርኤል ማርያምን ትፀንሲ ይላታል። ኸዚያ ልደቱን ትሥላለኸ። ልደቱን ስትሥል ሰብአ ሰገል እረኞቹም አሉ። ግዝረቱን ደሞ ቀጥለኽ መሣል ነው፤ ስምዖን አለ አሉ፣ አድግና ላሕም አሉ... ጌታን በትንፋሻቸው ያሞቁት፣ መልአኩም አብሮ ሚጠቀስ፤ ዓይኖቼ ማዳንህን ስላዩ በል ውሰደኝ ብሎ ጸልዮ
ይሞታል ። ኸዚያ ምሥጢረ ጥምቀቱ፣ ተአምራቱ፣ ቃና ዘገሊላው፣ አስተምህሮቱ አለ። ኸዚያ ምሥጢረ ቁርባንን ትሥላለህ፤ ሥቅለቱን አብረህ። ቀጥለህ ትንሣኤውንና ዕርገቱን ትሥላለህ። መጻሕፍት
በስንትና ስንት ምዕራፍ ያካተቱትን ታሪክ ሠዓሊው በጥቂት ብራናዎች አሣምሮ ቀምሮ ያስቀምጠዋል። ስለዚህ ምሥጢራቱን፣ የቱ ቀድሞ
የትኛው ሚከተል መሆኑን መመርመር ያስፈልጋል፤ የቀለም ማሳመር ብቻ ለሠዓሊነት አይበቃም።”

ጥላዬ፣ በተመስጦ አዳመጠና “እሺ የንታ፤ ንባቤንም ሥራዬንም
ተግቼ እቀጥላለሁ፤ ቃለ ሕይወት ያሰማልኝ” አላቸው፣ ትምህርታቸውን ከልቡ አዳምጦ።

“ዋናው ነገር እሱ ነው... ትጋት” አሉት፣ ሌባ ጣታቸውን እያወዛወዙ። “አንተን ትጉ ሁነህ አግኝቸኻለሁ። ምን ስጦታ ያለው ቢሆን ትጋት የሌለው ተማሪ አልወድም። ሥዕል ችሎታ ቢኖርህ ትጋት ኻላሳየህ ለሥራህ ጥሩ አይሆንም። አሁን በየቦታው ያሉት የተከበሩት ሠዓሊዎች አለሱ ሌላ ንሮ የላቸውም። አንዳንድ ተማሪ ይመጣል ኸኔ ዘንድ።እንዳው ብቻ ጫር ጫር አርጎ ቤተክሲያን ውስጥ ገብቶ ሥዕል
መሣል ይፈልጋል። ይኸ እንዴት ብሎ ይሆናል? ሥዕል ቀልድ ነው
እንዴ? እኔማ እንደዚያ ያለውን ተማሪ ኸኔ ዘንድ አላቆየውም። አንተ ለሥዕልም ለቤተክሲያንም አትሆንም ብየ ነው ምሰደው። ችሎታ አለ ትጋት ምንድርነው? አይምሰልህ ጥላዬ ሥራን ትልቅ ደረጃ ሚያደርሰው ትጋት ነው። እኔስ ብሆን አንድ ተማሪ ትጋት ካላሳየ ኸሱ ጋር ስለምን
እደክማለሁ? እስቲ በል ንገረኝ?”
“ውነት ነው... ውነት ነው” አለ፣ ጥላዬ ራሱን በአዎንታ እየነቀነቀ።

ልቡ ተነካ። ሥዕል እየሣለ ቤተክርስቲያንን ማገልገል እንዳለበት ይመኝ እንጂ፣ እንደዚህ ጠለቅ ብሎ ነገሩን አስቦበት አያውቅም።በአካባቢው የሚያያቸውን ቤቶች፣ ሰዎችና እንስሳት ቤታቸው ግድግዳ
ላይ ሲሥል ቢቆይም፣ የሚሥላቸውን ምስሎች ለዘላለም ቀርጾ ማስቀመጥ ከሚመኛቸው ነገሮች አንዱና ዋነኛው ምንትዋብን ነው። በተለይም
ደግሞ ነጠላ ተከናንባ ከቤተክርስቲያን ስትወጣ ያያት የነበረውን።

“ለሥዕል ያለኝ መውደድ ለብቻ ነው። ኸርሶ ዘንድ መማሬ ደሞ
ይበልጥ እንድወደው አድርጎኛል።”

“እኔም ለሥዕል ይኸ ነው ተብሎ ማይነገር ፍቅር አለኝ” አሉት።
“አለሱ ሌላ ሕይወት የለኝም። ሥዕል ሳይ እመራመራለሁ። የሠራሁትን ሥራ መልሼ ሳየው 'በውነት ይኸን የሠራኹ እኔ ነኝ ወይስ በኔ እጅ ራሱ ባለቤቱ ሣለው ብዬ እደነቃለኹ። ሥዕል የእዝጊሃር ወይም የደቂቀ
አማልክቱ ሥራ እንጂ የእኛ የደካሞቹ ፍጥረት አይመስለኝም። ጥላዬ...ሥዕል እኮ እንደ ቅኔ ከሳቴ ብርሃን ነው... የተደበቀውን ምሥጢር ሁሉ ሚገልጥ... ብርሃን ሚሰጥ። ለዝኽ ነው ቅኔን ብዙ ሊቃውንት ልሳነ መላእክት ነው ሚሉት።

ጥላዬ፣ መስማማቱን ለማሳየት ራሱን ነቀነቀ። “የንታ ሥዕል ለመማር እንደዛ ስመኝ ቆይቸ አሁን መማር በመቻሌ ዕድለኛ ሁኛለሁ።”

“ዕድል ኸሰማይ አይወድቅም” አሉት፣ ፊታቸውን ወደሱ መልሰው።
“ዕድል እንደ ሥዕል ነው። ሚገባው ዘንድ ነው ሚኸድ። ማይሆነው... ዝግጁ ሁኖ ማይጠብቀው ዘንድ አይኸድም። ወይም ማይሆነውን አይጣራም። ዕድል ልክ እንደ ሥዕል ሚፈልገውን ያውቃል፣ አውቆም
ይጣራል፣ ወይም ራሱ ወደሱ ይኸዳል። እንዳንተ ያለውን... የነፍሱን ጥሪ ሚያቀውን ኻለበት ፈልጎ ያወጣዋል። አንተም ዛዲያ ስትፈልገው፣ እሱም ሲፈልግህ... ስትፈላለጉ ቆይታችሁ ተገናኛችሁ።”

“አየ የንታ የእዝጊሃር ቸርነት ተጨምሮበት ነው።”

እዝጊሃር እኮ ማትችለውን አይሰጥህም። ጎበዝ ብትሆን ነው የሰጠህ።”

ውነት ነው አለ፣ ለራሱ።

“አሁን ይልቅ ምመክርህ” አሉት፣ ሌባ ጣታቸውን እያወዛወዙ፣ “ደብረ ወርቅ ኸደህ ሌሎች አስተማሮች ዘንድ መማርን ነው። እንደ ሌላው ትምርት ሁሉ ሥዕል እየተዘዋወርህ ስትማር ብዙ ትምርት ትቀስማለህ፣
ችሎታህንም ታዳብራለህ። ደብረ ወርቅ ታላላቅ የሥዕል መምህሮች
አሉ። እኔ እንደምታየው እያረዥሁ ነው። ኸንግዲህ እንደድሮው
ማስተማር አልችልም። አንተንም ገና ሳይህ ቀልቤ ስላረፈብህ
ተቀበልኩህ እንጂ ማስተማር እተዋለሁ እያልሁ ነበር” አሉት።

“የንታ ኸርሶ ዘንድ በቆየሁ። ኸርሶ መለየቱ ይከብደኛል።”

“ምን ይደረግ። እየደከመኝ መጣሁ።”

“ኸዝሁ ሌላ መምር ዘንድ ብቆይስ?”

“ሊቀጠበብት ኣዳሙ ዘንድ ነው እንድትማር የፈለግሁት። አዳሙ
ወደር ማይገኝለት መምህር ነው። ለኔም የረዥም ግዝየ ወዳጄ
ነው። እስታሁንም ብዙ ተማሮቸን ወደሱ ልኬያለሁ። አንተም ኸሱ
ዘንድ እንድትማር ነው ምፈልግ። ትምርትህን ስትጨርስ ተመልሰህ
ትመጣለህ።”

ጥላዬ፣ ጐንደር የዕድል በር ከፈተችልኝ፣ አለቃን መምህሬ፣ ጐንደርን ቤቴ ብሎ ተመቻችቶ ተቀምጦ፣ እንደዚህ ዓይነቱ ዱብ ዕዳ ሲመጣበት ደነገጠ፤ ሆድ ባሰው፤ መንፈሱ ተረበሸ፤ ተስፋ ሊቆርጥ ቃጣው።ከአለቃ ሔኖክ ሥር ሆኖ ታላቅ ሠዓሊ ለመሆን ያደረበትን ምኞት፣ከቤቱ ሲወጣ የሥዕል ንጉሥ ለመሆን የነበረውን ሕልም ሁሉ ጉም ሸፈነው። ደብረ ወርቅ ይሂድ ወይንም እዛው ጐንደር ሌላ አስተማሪ ዘንድ ይማር ለመወሰን አቃተው፤ ግራ ገባው። ምንትዋብን በአካል
ባያገኛትም እንኳ ከእሷ ርቆ መኖሩ ደግሞ አሳሰበው፣ አሳዘነው።....
።።።።።።።።።።፡፡።።።።።።።።።።።።

“ቁስቋም ብዙ ነገር ሰጥታኛለች፣ ወንድ ልዥ ደሞ ብትሰጠኝ።”
👍13😁1
አፄ በካፋ ሠራዊታቸው የሰፈረበት አሪንጎ ወይም የዕረፍት ቦታቸው ይባባ፣ አለበለዚያም ግብር አልከፍልም ያለውን ሊያስገብሩና
ወሰናቸውን ሊያስከብሩ በየቦታው ሲዘዋወሩ፣ ጣና አጠገብ ብርጊዳ
ገዳም ሲሄዱ፣ አደን ሲወጡ፣ እልፍኝ ገብተው ጉዳይ ሲፈጽሙ ወይም መሠሪ የተባለው ድብቅ ቦታ ገብተው ከመሣፍንትና ከመኳንንት ጋር ሲመክሩ፣ ምንትዋብና አያቷ ፋሲል ቤተመንግሥት አናት ላይ ያለው
ሰገነት ላይ ተያይዘው ይወጡና የቤተመንግሥቱን ዙርያ ገባውን
ይፈትሻሉ።

ሰገነቱ መላ ጐንደርንና ጣናን ከማሳየትም አልፎ፣ ወሬ ከሚለቅመውና ከሚያስፋፋው የቤተመንግሥት ባለሟል ጆሮ እርቀው ማውራት እንዲችሉ ይረዳቸዋል። ምንትዋብ ደግሞ ጠባቂዋ ከሆነውና በሄደችበት
እንደ ጭራ ከሚከተላት ጃንደረባ ራቅ ስለምትል ደስ ይላታል።

ከንድ ቀን እንደዚሁ ሰገነቱ ላይ ተቀምጠው ሲጫወቱ፣ “
እሚታዬ እኼን ጠዋት ላይ ሽቅብ ሚለኝን አልቻልሁትም። እስከመቸ ነው እንዲህ ሚተናነቀኝ?” ዐይኖቿን ጨፈን አድርጋ ወደ ኋላዋ ጋለል አለች።

“አይዞሽ እሱ ለግዝየው ነው፤ ይተውሻል። ብቻ ወንድ ያርግልሽ።
ጃንሆይም ቢሆኑ ይውደዱሽ እንጂ አይምሰልሽ አልጋ ወራሽ
ይፈልጋሉ።“

“ወንድ ሳልወልድ ብቀርስ?”

“ለቁስቋም ተይላት። ምን ግዝየም ቢሆን ከኛ ጋር ነች፤ አትጨነቂ።ይልቅስ... ያው... ቤተመንግሥት ወዳጅም ተቀናቃኝም ያለበት ማዶል? ማን ምን እንደሆነ ማወቁም ይጠቅማል” አሏት፣ ወሬውን
ለመለወጥ።

“እሚታዬ ትክክል ብለሻል። እንደምታውቂው” ብላ ጀመረች,
ወሬውን ስለቀየሩ ደስ ብሏት። “እንደምታውቂው ጃንሆይ ኸመሣፍነቱና ኸመኳንንቱ ጋር ምክር ሲይዙ እኔ አልገባም። ግና መሣፍንቱና መኳንንቱ ቤተመንግሥት መጥተው ኸሳቸው ጋር ሲጫወቱ አንዳንድ
ነገር አስተውላለሁ። አስተዋዮቹ እንዳይሰሙኝ” አለች፣ ወደ እንቁላል ግንቦቹ እያየች፣ ውስጥ የቆሙት ዘበኞች ይሰሙ እንደሆን ለማየት።

ስማቸውን ሳትጠራ፣ “እኛ” አለች፣ ዐይኗን ከወዲያ ወዲህ
አዘዋውራ፣ ልታወራ የፈለገችውን ሰውዬ በማስመሰል።

“እ... እ ገባኝ ማነን እንደምትይ።”

“አይገርምሽም? ነገራቸው ሁሉ ዙርያ።”

“እሳቸው ይቅር ላንቺ ለኛም ለትልልቆቹ ሰውን ጠንቅቀን እናውቃለን ለምንለው ግራ ናቸው።”

“እስቲ ፊታቸውን እዪ። አንድ ሰው አንድ ነገር ሲል ያነን የድመት
የመሰለ ዐይናቸውን ኸወዲያ ወዲህ ያቁለጨልጫሉ። ሰው ሚለውን በቅን ልቦና ማዳመጥ አይችሉ።”

ከዚያ በፊት እንደዛ ስትናገር ሰምተዋት አያውቁምና ተገረሙ። “ማን ነበር ስማቸው? እኛ ራሳቸው ገለጥ ያለው... እኛ ስንዝር ሚያህለት...?እኛ ማይጠዳቸው?”

“እሚታዬ ገብቶኛል ማነን እንደምትይ። ውነትሽን ነው፤ ፊታቸው አይፈታም። እሳቸው ዛዲያ ነገር ያሸንፋቸዋል ይባላል። ምላሳቸውም ብርቱ ነው። ኸኛ ቅድም ያልሁሽ... ኸሳቸው የባሱ ነገር ሽራቢ ናቸው።

ሁለቱ ደሞ ኩታና ቀሚስ ናቸው። ጃንሆይ ሁለቱንም አይወዱ። ሁለቱም ሚሉትን ከቁብም አያገቡ። ኸፈለጉ እኮ ኻገር ይነቅሏቸዋል። እንዳው
ችላ ብለዋቸው ነው እንጂ።”

“ልክ ነው።”

“እኝህ... ረዥሙ... ደጃማቹ... ደሞ አስመሳይ። ኸውስጥ ግን ኸኛ ኸጓደኛቸው... ገባሽ ማን እንደሆኑ?”

ዮልያና ራሳቸውን ነቀነቁላት ሰዎቹ ማን እንደሆኑ ማወቃቸውን
ለማመልከት። ብዙ ጊዜ አብረው ያይዋቸዋል።

“ዛዲያ ኸሳቸው ጋር ሚሸርቡት ያለ ይመስለኛል። ሁሌ ሺንሾኳሽሁ
ነው ማያቸው።”

“ሚዶልቱትን አያጡም። ወዳጅነት የገጠሙትም ለይሁ ይሆናል።
አሁን እየተረጋጋ መጣ እንጂ ጃንሆይ እንደነገሡ እኮ ብዙ አመጥ ነበር። ዛዲያ እኚ ረዥሙ በስንት አማላጅ ደሞም እግር ስመው ነው ጃንሆይ ይቅር ያሏቸው። እሳቸው ግና ኸውስጥ ሚጠነስሱት አያጡም።ያኔ ያመጡ ግዝየ ጃንሆይ ሌሎቹን እንደሚያረጉት እጃቸውን
ወይም እግራቸውን ያስቆርጧቸው አሊያም ያሰቅሏቸው ነበር። ብቻ
ኸመሣፍንቱና ኸመኳንንቱ ጋር መክረው ማሯቸው። እሳቸው ዛዲያ ይሉኝታ ባደረባቸው። ያነን ሁሉ መርበትበትና እግር መሳም ረስተው አሁንም አያርፉ፡፡”

“ከቤት እሚታዬ ጃንሆይ ግን እኼን እጅና እግር ሚያስቆርጡትን
ቢተዉ።”

“እንግዲህ...” አሉ፣ የሚሉት ጠፍቷቸው።

ገባትና ወሬውን ቀየረች። “እኛ ግጥሜ ናቸው ምልሽ የቅኔ ሊቁ...
እኛ ሁሌ ወዳቸዋለሁ ምልሽ... ምንም ውስጥ አይገቡ። ለጃንሆይም ታማኝ ናቸው” አለቻቸው።
“እሳቸው እኮ በትምርት የሰለጠኑ... ትምርታቸውንም ለመልካም ሚያውሉ ናቸው። እሳቸውና እኛ ጓደኛቸው ቄስ ገበዙ ምስጉን ሰዎች ናቸው። ለጃንሆይ ታማኝ ናቸው ላልሽው ታማኝነታቸው እኮ ለሳቸው
ማዶል፤ ለዘውዱ ነው። ዋናው እኮ ዘውዱ ነው። እሳቸውን ቢጠሉ
ስንኳ ለዘውዱ ታማኝ መሆን ይገባቸዋል። ንጉሦች እኮ ይመጣሉ፣ይኸዳሉ። ጥሩም ይመጣል፤ መጥፎም ይመጣል። ቀሪው... አገር አንድ ሚያረገው ዘውዱ ነው።”

በዝምታ ተቀመጡ።

ፈገግ አለችና፣ “እሚታዬ... እኔ መቸም አንድም ቀን ቤተመንግሥት ገባለሁ ብየ አስቤም አላውቅም። የት ብየ አስቤው? እዛው እቋራ
ላንዱ ትድሩኛላችሁ ብየ ነበር ማስብ እንጂ። መቸም ማን አሰበ
እኼን ሁሉ? አንቺ እንደዛ 'የተራ ባላባት ምሽትማ አትሆኚም' ስትይኝ ቤተመንግሥት ገባሁልሽ!” አለቻቸው።

“ያን ግዝየማ ቤተመንግሥት መግባት እንዴት ብለሽ ታስቢያለሽ? በያ ላይ ደሞ ሰው መቸም በሚኖርበት ልክ ነው ሚያስብ። ኻላየ...ኻላወቀ እንዴት ብሎ የሩቁን ያስባል? ለነገሩ እኔም ብሆን 'የተራ ባላባት ልዥ ምሽትማ አትሆኚም' ስልሽ መች ይኸን አስቤ! እንዲያው ቸሩ እዝጊሃር አንደበቴን ከፍቶ አናገረኝ! ግና ስንኳንም የኛን የሁነኝን
ልዥ አላገባሽ።”

ግንባሯ ተኮማተረ። “እሚታዬ ምን አረገ?”

“እኔ ኸልዥየው ጠብ የለኝም። አባትየው...”

“ያለፈ ነገር ነው። ስለሱ ማውራት ምን ያስፈልጋል?”

“የተራ ባላባት ልዥ ምሽትማ አትሆኚም አልሽኝ ብትይኝ ነዋ
ነገሩን ያነሳሁት።”በዝምታ ተቀመጡ።

እሷ ስለ አሁኑ ሕይወቷ ከሰማችበት ሰዐት ጀምሮ ታልመው የነበረው የሕይወት መንገድ አቅጣጫው መቀየሩ፣ ከጥላዬ... ከእዚያ የልጅነት
ፍቅሯ... ተራርቀው መኖራቸው ብቻ ሳይሆን፣ እሷ በወርቅ፣ በብር፣
ከፋርስ፣ ከህንድ፣ ከቱርክና ከየመን በመጣ ሐርና ምንጣፍ የተንቆጠቆጠ ቤተመንግሥት ውስጥ መኖሯ፣ ከካይሮ የመጣ ሐር መልበሷና ጊዜም ቢሆን ምንኛ ከዳተኛ መሆኑን መገንዘቧ ከንፈሯን አስመጠጣት፣ እንደ
መተከዝም አደረጋት። ከጥላዬም ጋር ቢሆን የሕይወታቸው ምዕራፍ
እንደተዘጋ አውቃ ባለበት ደሕና ይሁን፡፡ ቁስቋም እኼን ሁሉ ለኔ
እንደሰጠችኝ ለሱም ታስብለት አለችና ለአያቷ፣ “መቸም ዕድለኛ ነኝ”አለች።

“አንቺ ደሞ እናትሽን ይመስል ዕድል ዕድል ትያለሽ። ዕድል
ኸሰማይ ይወድቃል እንዴ? አታይም እንዴ አሁንስ ቢሆን ጃንሆይ ስላንቺ ያላቸውን ግምት? እንዳውስ ስላንቺ አውርተው ይጠግባሉ?እኼ ዕድል ነው በይኛ! ሚገባሽን ነው ያገኘሽው።”

“ቁስቋም ብዙ ነገር ሰጥታኛለች፣ ወንድ ልዥ ደሞ ብትሰጠኝ።”

“ትሰጥሻለች። ምን ይሳናታል? አሁን ስለሱ አታስቢ።”.....

ይቀጥላል
👍19
አትሮኖስ pinned «#ምንትዋብ ፡ ፡ #ክፍል_አስራ_አምስት ፡ ፡ #ድርሰት_በሕይወት_ተፈራ ...ጥላዬ፣ ከአለቃ ሔኖክ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እየመሠረተ ሲመጣ፣ብዙ ጊዜ አብሯቸው መቀመጥና መጫወት ሥዕል ከመሣል ቀጥሎ የሚያስደስተው ነገር ሆነ። ወደፊትም እንደሳቸው ጥበበኛ መሆን አበክሮ ተመኘ። ላደረጉለት ሁሉ ሲያመሰግናቸው ቢውል አላጠግበው አለ። “አለቃ ላረጉልኝ ሁሉ እመቤቴ ምላሹን ትስጥዎ” አላቸው፣ አንድ ቀን እንደወትሮዋቸው…»
#ያልታበሱ_እንባዎች


#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት


#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ


....አንዳንዴ የጊዜ ማጠርና መርዘም በሰዎች የውስጥ ስሜት የሚለካ ይመስላል ለተጨነቀ ልብና መንፈስ አንዱ አመት በአስራ ቤት የሚቆጠር ሲመስል ለተደሰተ ደግሞ የአንድ ቀን ያህል አጭር ይሆናል እሱ ግን አሁንም ኡደቱን ሳያዛባ እየሄደ ነው። እየነጎደ ነው።የቀንና የለሊት ፍርርቅ መሰረት አድርጎ ሳምንቱን በሳምንት ወሩንም በወር እየተካ ተምዘገዘገ። ብሎ ብሎ አንድ አመት አለቀና ሌላው ተጋመሰ
እነሆ አስቻለው አስመራ ከሄደ ሁለት ዓመት ከሶስት ወሩ! ሔዋን ክበረ መንግስት ከሄደች እንኳ አንድ ዓመት ከአራት ወር ሞላት። ሔዋን በክብረ መንግስት ታፈሡ በልሁና መርዕድ ዲላ ውስጥ እየኖሩ ይህ ጊዜ ከአስቻለው ትዝታና ናፍቆት ጋር በተያያዘ በተመሳሳይ የስሜት አቆጣጠር
እያሰቡት በመከራና በስቃይ ነው ያሳለፉት። አዝግሞ፣ ተጎትቶና ተንፏቆ ነው እዚህ የደረሰው። አንድ ክፍለ ዘመን ያህል ርቆባቸዋል። ለመምህርት ሸዋዬ ደግሞ በሚያስገርም ሁኔታ አጅግ አጭር ነበር።
ሸዋዬ በአስቻለውና በሔዋን መለያየት ቀድሞ የነበረባት የመንፈስ ቁስልወደ መገረን ተቀይሮ ከቅናት ስቃይ እፎይ ብላለች፡፡ ዛሬ የሁለቱ ፍቅር የዕለት
ተዕለት ሃሳብና ጭንቋ አይደለምና ፀሎቷ በዚሁ እንዲቀጥል ብቻ ነው። በሰላም የህይወት አጋጣሚ ውስጥ ገብታለች። ኑሮዋ ሞቅ ደመቅ እያለ ነው፡፡ ማህበራዊ ግንኙነቷም እየተሻሻለ ነው፡፡ ነቃ ነቃ ብላለች። የመንፈስ መረጋጋትም ይታይባታል። የአሁኑ ይዞታዋ ዘለቄታ እንዲኖረው ደፋ ቀና ማለቷን ተያይዛዋለች።
ለዚህ ሁሉ ሰበቡ የእናቷ ከክብረ መንግስት መምጣትና በአጭር ጊዜ ውስጥ ሔዋንን ይዘው ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ነበር። ያ አጋጣሚ በወቅቱ የእግር እሳት ሆኖ አንገብግቧት የነበረ ቢሆንም ለዛሬው ህይወቷ መሰረት ጥሉላት
ያለፈ በመሆኑ ግን በመልካም አጋጣሚነቱ እያስታወሰችው ትኖራለች።
የሔዋን እናት በሽዋዩ ቤት አድረው በነጋታው ወደ ሔዋን ጋ ከሄዱ በኋላ ከሸዋዬ ጋር ዳግም ሳይገናኙ ነበር ወደ ክብረ መንግስት የተመለሱት። በእርግጥ
መሄዴ ነውና ደህና ሁኚ' ሊሏት ከመሄዳቸው አንድ ቀን በፊት ወደ ቤቷ ጎራ ብለው ነበር፡፡ ግን አላገኟትም፡፡ ዕለቱ ባርናባስ ወየሶ በአንድ የሶሻሊስት አገር የውጭ ትምህርት ዕድል አግኝቶ ሊሄድ ሞቅ ደመቅ ባለ ድግስ የሚሸኝበት ቀን ነበርና ሸዋዬም የድግሱ ታዳሚ በመሆን ከድግሱ ቦታ አምሽታለች። የሔዋን እናት
ቶሎ የምትመለስ መስሏቸው ከወይዘሮ ዘነቡ ጋር እያወሩና እየተጫወቱ ቢጠብቋት
ቢቆዩም እሷ ግን እስከ ምሽት ድረስ ስለቆየችባቸው መልዕክቱ በወይዘሮ ዘነቡ በኩል እንዲደርሳት አድርገው ተመልሰዋል፡፡
ሽዋዬ የእናቷን ፈጥነው ወደ ክብረ መንግስት የመመለስ ጉዳይ ፈጽሞ ያሰበችው አልነበረም፡፡ በእሷ ግምት የሚሰነሳብቱና በዚያም አጋጣሚ የእሷንና
የሑዋንን ለየብቻ የመኖር ምክንያት ዋሽታም ቢሆን ቀጥፋ እውነታውን በመሽፈን
ልታወራላቸውና ራሷን ከተጠያቂነት ለማዳን የሚያስችሉ ብዙ መንገዶችን ፈጥራ ነበር፡፡ ግን ያ ካለመሆኑም በተጨማሪ እናቷ ከታፈሠ ጋር ውለው አድረው
እንዲሁም ከወይዘሮ ዘነቡ ጋር ብዙ ተጫውተው የመመለሳቸው ነገር ክፉኛ ነበር ያስደነገጣት፡፡ እነዚህ ሁለት ሰዎች የአስቻለውንና የሔዋንን ግንኙነት እንዲሁም እሷ በሁለቱ ፍቅረኛሞች ላይ የነበራትን አቋም እንዴት አድርገው ለእናቷ እንደሚገልጹላት ታውቃለችና በተፈጠረባት መጥፎ
አጋጣሚም እጅጉን ተበሳጭታም ተናድዳም ነበር፡፡
የእናቷን ወደ ክብረ መንግስት መመለስ ጉዳይ በስማችበት ወቅት የነበራት ምርጫ አንድ ብቻ ነበር። የጉዟውን ሁኔታ ታውቃለች፡፡ ዲላ ተነስተው በአለታ ወንዶ በኩል ነው የሚጓዙት። አለታ ወንዶ ሲደርሱ ከዲላ መኪና ላይ ወርደው ከአዲስ አበባ ወደ ክብረ መንግስት የሚሄደውን አውቶብስ መጠበቅ አለባቸው፡፡
በመሀል ቢያንስ ለሁለት ወይም ለሶስት ሰዓት ያህል አለታ ወንዶ ከተማ ይቆያሉ እናም ጠዋት ከዲላ ከተማ ተነስታ አብራቸው በመጓዝ አለታ ወንዶ
እስክሚደርሰብት ጊዜና በአለታ ወንዶ ከተማ በሚያደርጉት የቆይታ ጊዜ ውስጥ በወሬ ስትተከትካቸው ለመቆየት አስባ ይህንኑ ለመፈጸም ወስና አደረች::
በማግስቱ በጠዋት ተነሳች፡፡ እናቷን መሸንገያ የሚሆን ጥቂት ገንዘብ ቋጠረች። ወደ መናኸሪያው ገሰገሰች፡፡ ከእናቷ በፊት ቀድማ ከቦታው ደረሰች::
ሔዋን ከምትኖርበት አቅጣጫ ወደ መናኸሪያው በሚያመጣው መንገድ በርቀት ስትመለከት ስድስት ሰዎች ሲወጠ ታዩዋት። እየቀረቧት ሲሄዱ ማንነታቸውን
ለየች፡፡ እናቷ፥ ታፈሡ! በልሁ! መርዕድ፤ሔዋንና ትርፌ ናቸው፡፡ ዘንግታው እንጂ! ለካ እናቷ
መሸኘት ነበረባቸው:: ከተሸኙም በእነዚሁ ሰዎች ነው::ተበሳጨች፡፡ ከእናቷ ጋር በአንድ መኪና የመሳፈር ዕቅዷን ሰርዛ በተከታዩ ሎንችን ልትጓዝና እናቷን በአለታ ወንዶ ልትደርስባቸው፣ እዚያ በሚያደርጉት የቆይታ ጊዜ ብቻ ልታነጋግራቸውም ወሰነች፡፡ ለጊዜው በመናኻሪያው ውስጥ እንዳትታይ ወደ አንድ ሰዋራ ቦታ በመቆም የእናቷንና የሸኝዎቻቸውን እንቅስቃሴ መከታተል ጀመረች።

አሁንም የአላሰበችው ሁኔታ ተከሰተ፡፡ እሷ የምትጠብቀው የእናቷን መሄድ ብቻ ነበር፡፡ ግን ደግሞ ሔዋንም መኪና ላይ ወጥታ በመስኮት አንገትና እጇቿን
አውጥታ አፏን ቧ እድርጋ ከፍታ ምርር ብላ ስታለቅስና እጆቿን እያርገበገበች ታፈሡን ስትሰናበት አየች:: እነሱም አስከሬን ወደ ቀብር ቦታ ሸኝተው የሚመለሱ
ሀዘንተኞችን ያህል ምርር ብለው ሲያለቅሱና እጀቻቸውን እያርገበገቡ ሲሰናበቷት አየች።
«እንዴ! እሷም ልትሄድ!» አለች ሽዋዬ ለብቻዋ እየተነጋገረች። ገረማትም ደነቃትም:: ግን ለዕለቱ እቅዷ ምንም ዓይነት እንቅፋት እንደማይፈጥርባት ገመተች፣ እሷ ለእናቷ ስለሆነ ነገር ብታወራ በትዝብት ታዳምጥ እንደሆነ እንጂ
ሔዋን ደፍራ ክርክር እንደማትገጥማት ታውቃታለችና።
እነ ሔዋንና እናቷ በአለታ ወንዶ በኩል በሚሄደው አውቶብስ ተሳፍረው ከሄዱና ሽኝዎቻቸውም ከመናኸሪያው ወጥተው ወደየአቅጣጫቸው ከተበታተኑ በኋላ ሸዋዬ በቀጣይ ወደ አለታ ወንዶ የሚሄደውን መኪና ፍለጋ ጀመረች:: በእርግጥም
አንድ የመኪና ላይ ሰራተኛ የአንዲት አነስተኛ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በር
ከፍቶ «ወንዶ! ወንዶ! አለታ ወንዶ!» የሚል ጥሪ አሰማ። ሽዋዬ ወደ መኪናዋ ሮጣ
በመግባት የጋቢና ወንበር ይዛ ቁጭ አለች፡፡
ከአንድ ሠዓት አለፍ አለ፡፡ ያቺ መኪና ግን ቶሎ አልሞላ አለች፡፡ በዚያው ልክ ሸዋዬ ተበሳጨች ቸኩላ ጋቢና ወስጥ ቁጭ ብላ ፊትለፊት ስትመለከት በርካታ መንገደኛ ወደ መናኸሪያው ሲገባ ታያለኝ። ግን እሷ ወዴለችባት መኪና የሚገባው ሰው ከቁጥር አይገባም፡፡ ረዳቱ አሁንም "ወንዶ ወንዶ" እያለ መንገደኛ ይጠራል
ሸዋዬ ወደ ኋላ ዞር ብላ ስታይ ግን በርካታ ወንበሮች ክፍት ሆነው
ትመለከታለች: በዚያው ልክ ቀልቧ እየቆመ ትቁነጠነጥ ጀመር፡፡
ከመኪናዋ ወንበሮች ግማሽ ያህሉ በሰው ከተያዙ በኋላ ሹፌሩ ወደ መኪናዋ ገብቶ ሞተር አስነሳ፡፡ ነገር ግን ሞቅ ሞቅ ከአደረገ በኃላ ተመልሶ ሊወርድ ሲዘጋጅ ሸዋዬ አየችውና «በእናትህ ሾፌር መንገድ ላይ ትሞላለህ፥ እንሂድ» አለችው፡፡
👍6👏1
እንሄዳለን፡፡ አላትና ከመኪናው ላይ ወረደ:: ቁልፎቹን እያቅጨለጨለ
በመኪናዋ አካባቢ ይንጎራደድ ጀመር።
ሾፌሩ ጥቁርና ጠብሰቅ ያለ ሰውነት ያለው ነው: ቁመቱዎ ዘለግ ያለና ዕድሜዉ በሰላሳዎቹ አጋማሽ ላይ የሚገኝ አፍላ ጎልማሳ ነዉ:: የሰማያዊ ቀለም እጅጌ ጉርድ ሸሚዝ ለብሶ ጨፈቃ የሚያህል እጁ ሲታይ ጡንቻው ያስፈራራል። አልፎ አልፎ ከመኪና ላይ ሰራተኞች ጋር እየተላፋ በዚያ ክንዱ ጥምዝዝ እድርጎ ሲያስጮሀቸው እያየች ሸዋዬ በልሁ ተገኔ ትዝ ይላታል፤ ከመልካቸው በቀር የሰውነታቸው አቋም ተመሳሳይ ነውና።
ሰዓቱ ወደ አንድ ተኩል ሲጠጋ እንደ ምንም ጉዞ ተጀመረ። ያ ሠዓት ሔዋንና እናቷ ወደ አለታ ወንዶ መዳረሻቸወ ነው፡፡ ያ መንገድ ደግሞ የትራፊክ
ቁጥጥር ስለሌለበት በተለይ አነስተኛ ተሽከርካሪዎች ሰው በሰው ላይ እየጫኑ ሴንተርያ ተፈሪ ኬላ፣ ቀባዶ በተባሉና በሌሎችም ትንንሽ ከተሞች ሲደርሱ ተሳፋሪ
በማውጣት በማውረድ ጊዜ ያባከናሉ፡፡ አታካችና አሰልቺ መንገድ ነው፡፡ ሸዋዩ የተሳፈረችባት መኪናም ይህን ድርጊት ዘልላው አላለፈችም፡፡ ትቆም ትገተር ጀመር። ሽዋዬ በወጪ ወራጅ ጭቅጭቅ ጊዜው እያለፈባት ስትበሽቅ ስትናደድ ልቧ
ሊፈነዳ ደርሶ እያለለክች ልክ ከጠዋቱ አራት ሠዓት አካባቢ በአለታ ወንዶ መናኸሪያ ውስጥ ደረሰች፡፡ ወዲያው ዓይኗን በመናኸሪያው ዙሪያ ብታንከራትት
ሔዋንና እናቷ በአካባቢው የሉም። በእርግጥ ከአዲስ አበባ ወደ ክብረ መንግስት የሚሄደው አውቶብስ እዚያ መድረሻው ሰዓት ገና ነውና። በዚህ አጋጣሚ ሄዋንና
እናቷ ሻይ ቡና ለማለት ሄደው ሊሆን እንደሚችል ገምታ በመናኸሪያው አካባቢ የሚገኙትን ቡና ቤቶች በሙሉ ማሰስ ጀመረች፡፡ ነገር ግን እናቷና ሔዋን
አልታገኙም:: አሁንም እየተናደደች ፍለጋዋን ቀጠለች፡፡ ቢቸግራት እሷ በየቡና ቤቶች ስትሯሯጥ እናቷና ሔዋን በሌላ መንገድ ወደ መናኸሪያው ተመልሰው ይሆናል ብላ በማሱስ እንደገና ወደ መናኸሪያው ሮጠች:: ወደ ውስጥ ገብታ የመናህሪያውን ዙሪያ በዓይኗ ስትቃኝ በነበረችበት ወቅት ከበስተ ግራዋ በኩል የአንድ ወንድና ሴት ጭቅጭቅ ድንገት ከጆሮዋ ጥልቅ አለ፡
«አንቺ ባትዘገይብኝ ኖሮ እኮ እስካሁን ሄደን ነበር፡» በማለት ወንዱ በሴትዋ ላይ ይጮሃል።
ከአሁን በፊት ክብረ መንገስት የሚሄድ መኪና ይገኛል ብዬ እንዴት ልገምት?» አለች ሴትዮዋ::
«እንዴ! አለች ሸዋዬ እንደ መደንገጥ ብላ፡፡ ወደ ሰውየው ጠጋ በማለት «በቅርቡ ወደ ክብረ መንግስት የሄደ መኪና ነበር እንዴ?» ስትል ጠየቀችው።
«ሰው አጥቶ ሲጮህ ቆይቶ ከዲላ የመጣው አውቶብስ የሰው መአት
ሲዘረግፋለተ ግጥግጥ አድርጎ ጭኖ ሄደ፡፡» አላት ሰውየው እግረ መንገዱን ቁጭቱን ቀድሞ ለሚያነጋግራት ሴትዮ በመግለጽ ዓይነት፡፡
«ኣ» አለኝ ሸዋዬ ድንግጥ ብላ።
«ሙች ስልሽ!» ሰውየው አሁንም::
ሸዋዬ አንጀቷ ቁርጥ አለ። ከንፈሯን ንክስ አድርጋ በቁጭት ስሜት ራሷን ወዘወዘች በቃ! እናቷ ወይዘሮ ዘነቡና ታፈሡ የነገሯቸውን ሁሉ ተሸክመው ክብረ መንግስት ገብተዋል:: የብስጭቷ ብዛት ወገቧን አርገድግዶ ከአጥር ጥግ ድንጋይ ላይ አስቀመጣት። ራሷን በሁለት እጆቿ በመያዝ ወደ መሬት አቀረቀረች። ሀሳብ አወጣች አወረደች። ግን ምንም ማድረግ አልቻለችም፡፡
በዚያው ቦታ ላይ እንደተቀመጠች ሳታውቀው ሰዓቱ ሂዶ ኖሯል፡፡ ወደ
ስድስት ሰዓት አካባቢ ከአዲስ አበባ ወደ ክብረ መንግስት የሚሄደው አውቶብስ ደረሰና ጡሩንባውን እየነፋ ወደ መናኸሪያ'ው ገባ፡፡ እንደው ለምናልባቱ ብላ ወደ
መናኸሪያው በር ብትመለከትም ሔዋንና እናቷ ብቅ አላሉም፡፡ አውቶብሱ የሚያወርደውን አውርዶ የሚጭነውን ጭኖ ወደ ክበረ መንግስት ጉዞውን ቀጠሉ፡፡
የሸዋዬ ተስፋም ተሟጠጠ። ወደ ቤቷ በመመለስ በቀር ምርጫ አልነበራትም?
ወደ ዲላ ስለ መመለሷ ማሰብ ስትጀምር ቀደም ሲል ይታያት የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ትኩረት ወዳልሰጠችው ከቅጣጫ አተኮረች፡፡ ያቺ ከዲላ ይዛት
የመጣች ሊዮንችን እንደገና ወደ ዲላ ስትጭን ተመለከተች፡፡ ጠጋ ብላ ስትመለከት በመኪናዋ ውስጥ ሰው በሰው ላይ ተነባብሯል፡፡ የቆመው የተቀመጠው ተሳፋሪ አይተናነስም፡፡ ጨነቃት፡፡ ድንገት ወደ መናኸሪያው በር ዞር ብላ ስትመለከት ያን ወጠምሻ ሾፌር አየችው፡፡ አሁንም ቁልፎቹን እያቅጨለጨለ ከውጭ ወደ ውስጥ ይገባል። መኪናዋ አጠገብ እስከሚደርስ ጠበቀችና፡-
«የኔ ወንድም!» ስትል ጠራችው እንደ መሽኮርመም እያለች::
«አቤት!» እላት በጥቁር ፊቱ ላይ ወተት መስለው የሚታዩ ጥርሶቹን ፈገግ እያረገ፡፡
«መኪናህ በጣም ሞልቷል። እንዴት ይሻለኛል?» አለችው በመለማመጥ ዓይነት፡፡

«የመጣሽበት ጉዳይ አለቀ እንዴ?››
«ጨርሼ ነበር፡፡ መመለሻው ግን ጨነቀኝ::»
«እንደ ምንም ትሄጃለሻ!» አለና ሾፌሩ ወደ ረዳቱ ፊቱን መለስ አድርጎ
«እንዴት ነህ፣ ሞላ?» ሲል ረዳቱን ጠየቀው፡፡
«እየሞላ ነው::» አለው ረዳቱ የሚገባ ከተገኘ አሁንም ለመጫን የሚፈልግ መሆኑን በሚያመለክት አነጋገር፡፡
ሾፌሩ ሸዋዩንም ረዳቱንም ተውት አድርጎ ወደ ሌሉች ሰዎች ጠጋ ብሎ ያወራ ጀመር፡፡ ረዳቱ «ዲሳ ዲላ!» ማለቱን ቀጠለ፡፡ ሸዋዬ ግን ምናልባት ሾፌሩ ወንበር ፈልጎ ያስቀምጠኝ ይሆናል በማለት ቆማ ትጠባበቀው ጀመር። ከትንሽ
ቆይታ በኋላ ረዳቱ ሾፌሩን ተጣራ፡፡ ‹‹ማንዴ! ማንዴ! ግባና እንሂድ!» አለ፡፡
ሾፌሩ የረዳቱን ጥሪ በመቀበል ያወራቸው የነበሩትን ሰዎች ተሰናብቶ በመግቢያው በር በኩል ኸደ መኪናው ሲያመራ ሸዋዬ ከተል አለችና «ማንዴ እንዴት አረክልኝ ታድያ?» ስትል እንደ ማፈር እያለች ጠየቀችው ፡ የሾፌሩን ስም ከረዳቱ ጥሪ የወሰደችው ነው።
« አልገባሽም እንዴ?" አላት ሾፌሩ የራሱን መግቢያ በር ከፍቶ በእጁ ያዝ እያደረገ።
"መግቢያው ጨነቀኝ::»
ሾፌሩ ከመኪናወ ላይ ወጥቶ ከተቀመጠ በኋላ ወደ ኃላ ዞሮ ሲመስካት እውነትም መኪናው ሞልቶ ተጨናንቋል። መተንፈሻ የለም፡፡ ግን አንድ ነገር ትዝ አለው ሞተሩ ላይ ተቀምጠው ወደ ነበሩት ስዎች እየተመለከተ «እናንተ ተነሱ ሞተሩ ላይ መቀመጥ ክልከል ነው ወደ ኋላ! ወደ ኃላ ዳይ ዳይ» አላቸው፡፡
ሾፌሩ መሪ ይዞ የሚናገረው ሁሉ በተለይ በተቸገረ ተስፋሪ ዘንድ ተቀባይነት አለውና ሰዎቹ እያጉተመተሙ ቢሆን ተነሱ፡፡ ወዴኋላ እየተጋፋ ተሸጋሽገው
መቆማቸውን ከአረጋገጠ በኋላ ሾፈሩ ከመኪና ወርዶ ሸዋዬ
እንድትገባና ሞተር ላይ እንድትቀመጥ አደረጋት። ሸዋዬ ገባችና ፊቷን ወደ ሾፈሩ
አድርጋ እግሮቿን በማርሹ አጠገብ ኮርምታ በመቀመጥ ጉዞ ተጀመረ።
አስቸገርህ አይደል!» አለችው ሽዋዬ ሾፌሩ ማርሽ ሊቀይር ሲል እግሯ አወላክፎት የነበረ አጋጣሚን መነሻ በማድረግ።
«ምን ላድርግ፣ በሴት ልጅ አይጨክንም ብዬ ነዋ» አላት ሾፈሩ ቀና ብሎ በፈገግታ እያያት።
«ሁሉም እንዳተ በሆነ» አለች ሽዋዩ በመኪናው የፊት መስታወት ወዴፈት እያየችና ፈገግ እያለች፡፡ በዕለቱ ነጣ ያለ ሰማያዊ ኮትና ጉርድ ቀሚስ ለብሳለች:: ከጉልበቷ ጀምሮ እስክ ጡቷ ድረስ ሞላ ያለ ሰውነቷ በቀሚሷ ተወጥሮ ትርፁ
ይታያል። በዚያ ላይ አፍንጫ የሚሰነፍጥ ልዩ መዓዛ ያለው ሽቶ ተቀብታለች።
👍5