አትሮኖስ
286K subscribers
121 photos
3 videos
41 files
570 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
ግን መዝረፍ እና ማጅራት መምታት ሁሉ ልትጀምር እንደምትችል በቀልድ እያስመሰለችም ቢሆን ታወራለች..ይህ ሁሉ ካልተሳካላት የመጨረሻ ምርጫዋ ግን ሀብታም ባል አግብታ ሀብታም መሆን ነው፡፡ በአቋራጭ መክበር ይሏችሆል እንዲህ ነው፡፡
ሮሚ ያው እንደነገሪኮችሁ ቀለሜዋ ነች ..አሁን የህክምና የ5ኛ ዓመት ተማሪ ነች፡፡ ለዛውም የእውነት ሰቃይ ተማሪ፡፡እርግጥ እንደአጀማመሯ አሁን ስድስተኛ አመቷ ላይ መሆን ነበረባት፡፡ግን ሶስተኛ አመት እያለች ዊዝድሮዋል ለመሙላት እና አንድ አመት ለማቋረጥ ተገዳ ነበር ..ለምን ብትሉ….? አርግዛ፡፡ምክንያቱም እሷ ወንድን ማመን እና በቅጽበት ለፍቅር ዝልፍልፍ ማለት ዋና ድክመቷ ነው… ፡፡እናም አሁን የሦስት አመት ልጅ አላት….ማክዳ እንላታለን፡፡በዚህ ጉዳይም ከፌናን ጋር ይላያያሉ ያቺኛዋ ቆቅ ነች …ከዛም ከዛም ጋር ስቃና ፎግራ ዞር ማለቱን ተክናበታለች፡፡
ማክዳ ያው እንደነገርኮችሁ የእህቴ የሮማን ልጅ ናት፡፡ቤታችንን እና አለማችንን ከተቀላቀለች ገና ሶስት አመቷ ቢሆንም ታሪካዊ ለነበረው ቤተሰብ ሌላ ታሪክ ጨምራበታለች…..ሌላ ድምቀት ሌላ ደስታ..ሌላ ፍንደቃ..በተለይ ለእናቴ...ምንም ቢሆን የመጀመሪያዋ የልጅ ልጇ አይደለች፡፡
አሁን የቀረውት እኔ ነኝ ፡፡ቆይ ስለእኔ ማውራት ከመጀመሬ በፊት ለካ አባት የሚባል ነገር አለ ፡፡የሁላችንም አባት አንድ ሰው ነው፡፡ከእናቴ ጋር በትዳር 8 ዓመት ከቆየ ቡኋላ ተፋተዋል..የፍቺያቸው መንስኤ እኔ ነኝ…፡፡በእኔ ጉዳይ ላይ መስማማት ስላቃታቸው ለመለያየት በቅተዋል…አሁን የት እንዳለ በትክክል አላውቅም ..ማወቅም አልፈልግም …ቢሞት ሁሉ ግድ ያለኝ አይመስለኝም…፡፡…በነገራችን ላይ አንዳንዴ ሳስብ እናቴን ያለ ባል ወንድምና እህቶቼን ያለአባት ስላስቀረዋቸው ውስጤን ይደማል፡፡….መላ ቤተሰቡ ለእኔ ሲል የከፈለውን መስዋዕትነት ሳስብ ምነው ባልተፈጠርኩ ኖሮ ምልባቸው ቀናቶች ብዙናቸው…በጣም ብዙ፡፡
እስቲ ስለራሴ እንዲሁ ለትውውቅ ያህል ጥቂት ላውራችሁ፡፡ስሜ ብዙ ነው፡፡እዬብ፣በእሱ ፍቃድ ፤ፀጋ፤ ኪያ እኚ ሁሉ ስሞች ከኪያ በስተቀር የወጡልኝ በእናቴ ነው…ኪያ እህቴ ፌናን ያወጣችልኝ ስም ሲሆን አሁን እቤት ውስጥ አብዛኛው ሰው አዘውትሮ የሚጠቀመው ይሄንን ስም ነው፡፡አሁን 22 ዓመቴ እንደሆነ የነገርኳችሁ መሰለኝ፡፡ትምህርት አልተማርኩም..እንዳይደናገራችሁ አልተማርኩም ስላችሁ መሀይም ነኝ ማለቴ አይደለም፡፡ግን መደበኛውን የትምህርት ስርዓትና ቅደም ተከተል በጠበቀ መልኩ አንደኛ ሁለተኛ እያልኩና ትምህርት ቤት እየተመላለስኩ የመማሩን እድል አላገኘውም፡፡ግን አሁን የጠቅላላ ዕውቀት ፈተና ብፈተን አንድ ጎበዝ ከሚባል ዲግሪ ምሩቅ ጋር የተመጣጠነ ክህሎት እንደሚኖረኝ እተማመናለው፡፡ይሄ ክህሎት በቀልድ የተገኘ አልነበረም እናቴ ያለፉትን አስራ አምስት አመት ለፍታ አስተምራኛለች፡፡ማለቴ ለብቻዬ..እቤት ውስጥ….ግራ ተጋባችሁ አይደል…..?፡፡
አሁን በዚህን ወቅት ሰማያዊ ቀለም ያለው ለስለስ ያለ ሙሉ ቢጃማ ለብሼ ከቤታችን ጓሮ ካለው ጽዱና በአበቦች በተከበበው አፀድ ውስጥ ዊልቸር ላይ ተቀምጬ የጥዋት ፀሀይ በተመስጦ እየሞቅኩ ነው …፡፡እግሮቼ የዊልቸሩ እግር ተደግፈው ልፍስፍስ ብለው ይታዩኛል…. ቀኝ እጄ እናቴ ቅድም እዚህ ቦታ ስታመጣኝ የዊልቸሩ እጀታ ላይ አስተካክላ እንዳስቀመጠችው እዛው ባታ እንደዛው ተልፈስፍሶ ተቀምጧል፡፡ደካማው አንገቴ ጭንቅላቴን ሙሉ ለሙሉ መሸከም ስለማይችል ዝንብል ወደለበት ወደግራ በኩል ለሱ ተብሎ በተሰራለት መደገፊያ ላይ ደገፍ ብሏል …የተከፈተ አፌን መክደን ተስኖኝ ለሀጬ መዝረክረኩ ለእኔው እየታየኝ በራሴው ፈገግ ለማለት እየሞከርኩ ነው፡፡
ከሰውነት ክፍሎቼ ያለማንም እርዳታ በነፃነት መንቀሳቀስ የሚችሉት ዓይኖቼ እና ግራ እጄ ብቻ ነው፡፡በግራ እጄ እበላለው…. በግራ እጄ ዊልቸሬን በመጠኑ ማንቀሳቀስ እችላለው..በግራ እጄ እጽፋለው…በግራ እጄ በምልክት ከቤተሰቦቼ ጋር ለመግባባት እሞክራለው…እናም ደስታኛ ነኝ፡፡መቼስ ደስተኛ ነኝ ስላችሁ ምፀት ይመስላችኃል አይደል...?እውነቴን ነው፡፡ለዚህ ማንነቴ የበቃውት በተአምር እና በእናቴ የዘመናት ትጋት ነው፡፡ቢያንስ እኮ የምጠቀምበት አንድ እጅ አለኝ ..ይሄ እጄ ደግሞ መንቀሳቀስ ከጀመረ ገና ሶስተኛ አመቱ ነው…አይኖቼ ከበፊቱም በደንብ አጥርተው ያዩልኛል..ጆሮዎቼ ከብዙ ርቀት አጥርተው ይሰሙልኛል..አዕምሮዬ ጥርት አድርጎ ነገሮችን ማገናዘብና መመራመር ይችላል…፡፡
እዚህ ላይ ከሁሉም በላይ እኔ ማሰብ እንደምችል አካባቢዬ ያሉ ሰዎች ሁሉ ማመን ከጀመሩ ገና አምስት ስድስት አመታት ቢሆነው ነው፡፡ከዛ በፊት ለሁሉም ሰው አዕምሮዬም እንደአካሌ የበደነ እንደሆነ ነበር የሚገምቱት… ከእናቴ በስተቀር..፡፡
እንደነገርኳችሁ ከአምስት አመቴ ጀምሮ እናቴ ጭኗ ላይ አስተኝታ ፀጉሬን እያሻሻች መፅሀፍ ታነብልኝ ነበር… ያንን የሚያስተውሉ ዘመድ ወዳጆች ግን እሷም ማበዷ ነው ይሏት ነበር..እና በትራስ ደራርባ በማስደገፍ ከፊቴ ጥቁር ብላክ ቦርድ ሰቅላ ከአምስት አመቴ ጀምሮ ሀ..ሁ..ሂ እያለች ያለመታከት ስታስጠናኛ…A,B.C….ስታለማምደኝ 1..2..3..እያለች ስትደጋግምልኝ..ሁሉም ሰው የሚያስበው ጋንኤል እንደለከፋት ነበር
…እኔ እንደዛሬ ግራ እጄን እንኳን ማንቀሳቀስ አልችልም ስለነበር… በምልክት እንኳን ገብቶኛል አልገባኝም ብዬ አላረጋግጥላት አልችልም ነበር..አንገቴንም› እንኳን ሙሉ በሙሉ ለማዘዝ አልችልም ነበር…..ከእነዛ አይኖቼ የሚወጡት የብርሀን ጨረሮች ግን ከእናቴ ጋር ለመግባት በቂ ነበሩ…የምትለውን እንደምሰማትም እንደምረዳትም ከአይኖቼ ውስጥ አንብባ ታውቅ ነበር…እናቴ ትምህርት ቤት ባይሎጂ እንደምታስተምር ነግሬያችሁ ነበር… እቤት ግን እኔን ሁሉንም ትምህርት ደራጃውን በጠበቀ ጥራት ታስተምራኛለች….አሁንም ድረስ መናገር አልችልም፡፡ግን ሶስት ቋንቋ በደንብ አጥረቼ ሰማለው..እፅፋለው፡፡እድሜ ለእናቴ…
እንግዲህ ወደ ዋናው የቤተሰባችን ታሪክ ለመግባት ከእናቴ የወጣትነት ጊዜ ጀምራለው…. የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሳለች ጀምሮ ያለውን…...

💫💫ይቀጥላል💫💫

አብሮነታችሁ ያበረታናል Like 👍 በማድረግ አብሮነታችሁን አሳዩን
ማንኛውንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍8😁1
#ሀርሜ_ኮ
:
ክፍል-2

:
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

...ይሄ ታሪክ እናቴ እና አባቴ እንዴት እንደተዋወቁ የሚያትት ነው፡፡ታሪኩን የነገረችኝ እናቴ ነች፡፡እርግጥ ታሪኩን አንድ ጊዜ ብቻ ሳይሆን በስድስት ወር እና በዓመት ልዩነት አቀራረብን ለወጥ እያደረገች የተወሰነውን እየቀነሰች እና በፊት ነግራኝ ከነበረው ውስጥ ያልተካተተ አዲስ ታሪክ እየጨመረችበት ነግራኛለች፡፡እናቴ ስለአባቴ የምታወራኝ ብሶት ሲሰማት ነው..ውስጧን ሀዘን ሲቦረቡረው ነው…ልቧ ውስጥ ያለ ጥልቅ ባዶ ሽንቁር ሲረብሻት ነው፡፡የዛን ጊዜ ትናንቷን ታስታውሳለች፤የድሮ ፍቅሯ ትዝ ይላታል፡፡የዛን ጊዜ አባቴን ታስታውሳለች፤የዛን ጊዜ የሚያዳምጣትን ሰው ትፈልጋለች፤ለማዳመጥ ደግሞ በዚህ አለም ላይ ከእኔ ከልጇ በላይ ችሎታ ያለው ሰው የለም..ድንቅ የተባልኩ አድማጭ ነኝ የማንንም ንግግር አላቋርጥም ደግሞም ሚስጥር ጠባቂ ነኝ ..ማንም የፈለገውን ነገር ለእኔ ቢነግረኝ በቃ ለአምላኩ በሽኩሽኩታ እንደነገረው መቁጠር አለበት.ስለዚህ የቤታችን አባል መተንፈስ እና እፎይ ማለት ሲያስፈልጋቸው ወደ እኔ ነው የሚሮጡት..ይህ እናቴንም ያጠቃልላል፡፡
እና ይሄንን ከአባቴ ጋር የነበራትን የፍቅር ታሪክ ደጋግማ ስለነገረችኝ ልክ በእያንዳንዷ ግንኙነታቸው ወቅት አብሬያቸው የነበርኩ መስሎ ነው ሚሰማኝ …ሁሉ ነገር ልክ አሪፍ ደራሲ እንደደረሰው መሳጭ የፍቅር ድርሰት ፍንትው ብሎ ይታወሰኛል፡፡
የተገናኙት ሁለቱም የአዲስ አበባ የአንደኛ አመት ተማሪ እያሉ ነው፡፡እሱ የኬሚስትሪ እሷ የባይሎጂ ዲፓርትመንት ተማሪ ነበሩ …ያው ፍረሽ ማን ላይ ሁለቱም የሚወስዱት ተመሳሳይ አይነት ኮርስ ነበረ እና የገና ማዕበል ለማምለጥ ሁሉም ተማሪ በፍራቻ ተውጦ፤በስጋት እየተናጠ አንገቱን አቀርቅሮ በየዩኒቨርሲቲው ጥጋ ጥግ እና በላይብረሪው ከወረቀት ጋር እራሱን አጣብቆ ፍዳውን በሚያበት ወቅት ነበር..በተለይ መምህሩ አንብቡ ብሎ የጠቆማቸውን መጽሀፍና፤ሲኒየር ሚባሉት ተማሪዎች ለፈተና ያንን መጽሀፍ አንብቡት ብለው የጠቆሙትን መጽሀፍ ለማግኘት ላይብረሪ ውስጥ ያለው መራኮት እና መሻማት ያስቃልም .ያስተዛዝባልም፡፡ በተለይ የፈተናው ወቅት እየተቃረበ በመጣ ቁጥር ውጥረቶቹ በዛው ልክ እየከረሩ ይሄድ ነበር፡፡
በዚህ ወቅት ነው እንግዲህ ሞጋስ ባሴ የተባለው ከጎንደር አርማጭኦ አካባቢ ብዙ ኪሎ ሜትሮችን አቋርጦ የመጣው ወጣት በዚህ መራኮት ውስጥ በመደነጋገርም ቢሆን መፋለም ጀምሮ የነበረው..ግን ሁሌ ተሸናፊ ነበር…፡፡ካደገበት ማህበረሰብ የወረሰው ይሉኝታ ለተሸናፊ እንዲዳረግ አመቻችቶታል፤ከመናጠቅ ይልቅ መካፈልን ነበር የሚያውቀው ጓደኛን ወደ ኃላ ስቦ በማስቀረት ወደ ፊት ከመሸምጠጥ ይልቅ አንተ ቅደም ወንድሜ ብሎ ከመንገድ ገለል ብሎ ሌላውን የማሰቀደም ስነ ልቦና ነበር የነበረው፡፡ንጽህ የዋህነት፤የጠራ ሰባዊነት የግል ንብረቶቹ ነበሩ…፡፡ግን አዲስ አበባ ሌላ ነው፡፡እርግጥ ከእሱ ጋር ተመሳሳይ የሆኑ ብዙ የክፍለሀገር ልጆች ነበሩ..ግን በተለይ በመጀመሪያው አመት የሚደምቁትና ፈካ ብለው የሚታዩት የትላልቅ ከተማ ውልዶቹ ናቸው፡፡አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ..በምዕራባዊውና በምሰራቃዊው ፍልስፍና መካከል የሚዋልል ከተሜን በውስጧ የያዘች መንጠቅ እንደብልጠት፣መቅደም እንደአራዳነት የሚታይባት የተለየች ቦታ ..እና አንድ መጽሀፍ ለማግኘት ለ5 ቀን የላይብረሪውን ደጅ ፀንቶ ነበር..አልቀናውም እንጂ..፡፡
‹‹አረ ወዲያ….›› እያለ ላይብረሪውን ለቆ በቅሬታ ሲወጣ ..ያንን የሰሙ ሌሎች እኩዬቹ ሲገለፍጡበት ለሶስት ቀን የታዘበችው እናቴ ታዝባ ቅር ብሎት ነበር…በአራተኛው ቀን ግን ከተቀመጠችበት ወንበር ላይ ሳትንቀሳቀስ በምልክት ጠራችው..እሷ ወደ ተቀመጠችበት መቀመጫ ግራ በተጋባ እይታ ተገትሮ ሲያማትር መልሳ በእጇ ምልክት ጠራችው…፡፡በንዴቱ ውስጥ ቢሆንም…ወደ እሷ ተጠጋ..ስሯ ደረሰ….
‹‹ተቀመጥ አለችው…››በሹክሹክታ
‹‹ምን ይሁነኝ ብዬ….?.››መለሰላት ከእሷ ትንሽ ከፍ ባለ ድምጽ ሌሎችን የላይብረሪ ተጠቃሚዎችን እንዳይረብሹ በመስጋት ግራና ቀኝ በመሳቀቅ ተመለከተችና‹‹ ቁጭ በል›› ብላ ልክ ከዚህ በፊት በደንብ እንደምታውቀው የቅርብ ጓደኛዋ እጁን በመያዝ ስባ አስቀመጠችውና‹‹ይሄን አይደል የፈለከው …እንካ አንብብ››ብላ ስታነበው የነበረውን መጻሀፍ ወደ እሱ ፊት አስጠጋችለት ….ማመን አልቻለም..አንዴ መፅሀፉን ..አንዴ ልጅቷን እያፈራረቀ ማየት ጀመረ
‹‹አጥና እንጂ… ለዚህ መጽሀፍ አይደል ሳምንቱን ሙሉ ስትበሰጭ የሰነበትከው…..?እኔ በቂ ቀን አግኝቼ ማየት ያለብኝን ያህል አይቼዋለው ዛሬ ደብተሬን ነው የማነበው…››
‹‹ታዲያ እማታነቢው ከሆነ ለምን ታቀፍሺው.? ››በብስጭት
‹‹ለአንተ ብዬ.››
‹‹አረገኝ…..?.›.›
‹‹ባክህ ታጠና እንደሆነ አጥና …ካልፈለግክ መጽሀፍን አምጣው..››ለራሷም ባልታወቃት ስሜትም በቁጣ መለሰችለት፡፡…. እንግዲህ የመጀመሪያ ትውውቃቸው እንዲህ ነበር የጀመረው፡፡
እርግጥ ሁለቱም ኢትዬጵያዊ ይሁኑ እንጂ በተለያየ አካባቢ እና ባህል ውስጥ ነው ያደጉት ፡፡ ቢሆንም ይሄ ልዩነታቸው ለግንኙነታቸው እንቅፋት አልሆነባቸውም..እናቴ ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት በምትገኘው አዲስ አለም ከተማ ተወልዳ ያደገችና ሀይስኩል ስትደርስ ወደአዲስ አበባ ሙሉ በሙሉ ገብታ ተምህርቷን የጨረሰች በመሆኗ ከተሜነት ሲያጠቃት አባቴ ግን ከአነስተኛ የገጠር ከተማ በመውጣቱ በተቃራኒ ስሜት ውስጥ ያለ ነበር..
ከዛን ቀን ወዲህ ለሁለተኛ ጌዜ የተገናኙት አንደኛ ሴሚስተር ፈተና ተጠናቆ የፈተና ውጤቱ ታውቆ ውጤቱም ቦርድ ላይ ተለጥፎ ተማሪ እየተተረማመሰ በሚያበት ጊዜ ሁለቱም ከትርምሱ ውስጥ የየራሳቸውን አይተው ሲወጡ እርስ በርስ በመላተማቸው ነበር…ዞር ብላ ስታየው ማንነቱ ትዝ ስላላት ‹‹…አንተ››አለቸ
‹‹አንቺው…አለሽ ኖሮል.? ››
‹‹ምነው ፈልገሀኝ ነበር እንዴ.?››ይሄንን የሚያወሩት ከተማሪዎቹ አጀቡ ተገንጥለው በመውጣት ብቻቸውን ጎን ለጎን እየተራመዱ ነበር
‹‹እሱማ አልፈለግኩሽም…በሀሳቤ ተሰንቅረሺብኝ እንጂ››
‹‹ምን ተሰንቅረሽብኝ..ማ.. እኔ .?››እናቴ በመገረም
‹‹እንደእሱም ማለቴ እማየደል.?››
‹‹እና እንዴት ማለት ነው.?››
‹‹በቃ ተይው…ለመሆኑ ፈተናይቱን እንዴት ሆንሽ…..?››
‹‹አሪፍ ነው...አንተስ….?››
‹‹እኔማ ጥሩ ነው.. እንዲሁ ባልፈራ ኖሮ የተሸለ አመጣ ነበር…ወይኔ ወንድ በሀገሬ መውዜር እና ምንሽር ቢደቀንብኝ ማልበረግግ ዠግና እዚ በወረቀት ተለቅልቆ ለሚመለስ የፈረንጄ ወሬ ልንቦቅቦቅ…...?››
ከዚህ ቡኃላ ግንኙነታቸው በጓደኝነት ይቀጥላል …ሁለተኛ አመት ግምሽ ድረስ ተመሳሳይ ይሆናል…አብረው ያጠናሉ…አብረው ከተማውን ይዞራሉ…ሚስጥር ይጋራሉ፡፡
ነገሮች የተቀየሩበት ቅጽበት አባቴ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ሁለት አመት ሲማር ከዕውቀቱ ይልቅ አራዳነቱ ላይ ከፍተኛ ለውጥ አሳይቷ ነበር .ከንግግሩ ቀልጠፍ፤ከአለባበሱ ዘነጥ፤ካረማመዱ ጀነን ማለቱ ለሌላ ሰው አይደለም ለሱ ለራሱ ይታወቀው ነበር…አሁን ከየዋህነት ይልቅ ብልጠትን፤ከመበለጥ ይልቅ መሸወድን፤ከመግደርደር ይልቅ አይን አውጣነትን፤ተጎትቶ ከመቅረት ይልቅ ጎትቶ ማለፍን እለት ከእለት ከመደበኛ ትምህር እኩል እንደውም ከእዛም በላይ እየተለማመዳቸው የህይወቱ አንድ ክፍል አድርጎቸው አድርጓቸው ነበር የእኛ ስልጣኔ እንዲህ አይደል?እና እናቴንም በተመለከተ ሳይቀደም ሊቀድም ወሰነ በአንድ እለተ እሁድ የረፍት ቀን በወቅቱ ዝነኛ ወደ ነበረው እና ዘፋኞች ሁሉ የቪዲዬ ክሊፓቸወንን ወደሚያስቀሩጽበት ብሄረ-ጽጌ መናፈሻ ሳታስብ ወሰዳት
👍14😁1
በጣም ነበር ያሰደመማት..ምናልባት ለአሁን ጊዜ ዬኒቨረስቲ ተማሪ ሻራተን እና ኮንትኔታል መጋበዝም ቢሆን ብርቅ ላይሆን ይችላል…አለፍም ካላም ባህር ተሸግሮ ድንበር አቋርጦ አየር ሰንጥቆ ዱባይና ኢስታንቡል ቅዳሜና እሁድን ማሳለፍ እንደው ትንሽ ጉራ ለመንዛት ይጠቅም ይሆን እንጂ ያን ያህል አፍ የሚያስከፍት አይደለም..የዛን ጊዜ ግን ለአንድ ሴት ሻይ ቤት ወንበር ላይ ለዛውም ከጎረምሳ ጋር ቁጭ ብሎ ቀይ ሻይ መጠጣት በአሁን ጊዜ በአደባባይ ሀሽሽ እንደማጬስ ያህል ነውር ነበር…ለሁለቱም እንደዛ አይነት ቦታ ሲገቡ የመጀመሪያ ቀናቸው ነበር…በዛፎች በተከበበውና አረንጎዴ በለበሰው ግቢ ውስጥ አንድ ነጠል ያለ ቦታ ፊት ለፊት ቁጭ ብለው ሚርንዳቸውን እየጠጡ ማውራት ቀጠሉ
‹‹እንዴት ይሄን ቦታ አወቅከው.?››
‹‹ሰው አሳይቶኝ››
‹‹ከዚህ በፊት መጥተህ ነበር››
‹‹አልገባውም…ከውጭ ነው ያየውት››
‹‹እንዴት እዚህ ደርሰህ ሳትገባ ተመለስክ ››
‹‹ካንቺ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ማየት ስለፈለግኩ..ቀድሞ መግባት አላሻኝም፡፡››
‹‹አመሰግናለው…አንተእኮ ምርጥ ጓደኛዬ ነህ››
‹‹ጓደኛዬ ስትይ?››
‹‹ጓደኛዬ ነዋ…ጓደኛ አታውቅም››
‹‹እናም ጓደኛሽ ብቻ ነኝ…››
‹‹አይ አባቴም ነህ››ሀሳቡን ብትጠረጥርም ያልገባት መስላ ቀለደችበት
‹‹እኔ ቀልድም አይደልም ማወራው..ስላንቺ ሳስብ ልቤ ፍርፍር ነው ምትልነብኝ፤ውስጤ እርብሽብሽ ይላል፤እኔ ወዳጄ እንድትሆኚ ነው የምፈልገው››
‹‹ወዳጂ..ምን ማለት ነው?››
‹‹የወደፊት ሙሽራዬ እንድትሆጎኚ እፈልጋለው…እኔ ካንቺ ተለይቼ መኖር አይሆንልኝም…እምቢ ብትይኝ እንኳን ሞጭልፌም ቢሆን የራሴ አደርግሻለው››
እናቴ በገረሜታ‹‹ሞጭልፌ ስትል?››
‹‹ምኖ ነሽ ባክሽ ..አይገባሽም፡፡እጠልፍሻለው እያልኩሽ ነው….››
ከብዙ ማብራሪያና ልመና ቡኃላ ‹‹ላስብበት›› አለችው ፡፡በዛን ጊዜ ላስብበት ማለት ያው ግማሽ እሺታን ይወክል ነበር..አባቴ ፈነጠዘ…ለሚቀርቡት ሁሉ አዋጅ አስነገረ…የመጨራሻው መልስም እንደገመተው እሺ ሆነ …መቼስ በሴት ፍቅር የተማረከ የወንድ ልብ ነፍሱንም ጭምር አሳልፎ ቢሰጥ የሚገርም አይሆንም እና ሁለቱም እንደተመረቁ አዲስ አባባ ነበር ስራ መፈለግ የጀመሩት ያው የትምህርት ውጤታቸው ሁለቱም አሪፍ የሚባል ስለነበረ ወዲያው ነበር በአስተማሪነት አንድ ትምህር ቤት የተቀጠሩት….
ከሁለት ወር ቡኃላ ነበር የተጋቡት….ይሄ አሁን ያለንበትን ቤት አያቴ ነው ማለቴ የእናቴ አባት የሰርግ ስጦታ ገዝቶ ያበረከተላቸው…ይሄ ሲሆን ደግሞ ከዛ እናቴ እንደነገረችኝ ሁሉ ነገር ፍጽማዊ ይመስል ነበር፡፡..ሲጋቡ፤ ሲዋሀዱ፤አንድ መሶብ ቆርሰው አንድ አልጋ ላይ ለሊቱን ሲያሳልፉ በአለም ላይ ያለው ደስታ ሁሉ ተጠራርጎ እቤታቸው ገብቶ ነበር፡፡..እናቴ በስድስት ወሯ አረገዘች፡፡ይሄ ደግሞ ሌላ ደስታ፤ሌላ ፈንጠዝያ በቤታቸው እንዲዘንብ ተጨማሪ ምክንያት ሆነ..፡፡ቀኑ ደርሶ እናቴ ስትወልድ ሁለት መላአክ የመሰሉ መንትያ ሴቶች፡፡…እናቴ አንዷን ፌናን ብላ ስታወጣላት ሌላኛዋን ደግሞ አባቴ ሮዛ ብሎ ሰየማት፡፡መነጋገሪያና ደስታኛ ቤተሰብ ሆነ፡፡እህቶቼ ሁለት አመት ሞልቶቸው ድክ ድክ ማለት ሲጀምሩ እኔ ተረገዝኩ፡፡ አሁንም ሌላ ደስታ ፡፡ሁሌ ሳቅ የሞላበት ቤት፤ሁሌ ጫወታ የደራበት ቤት፤ሁሌ ፈገግታ ማይነጥፍበት ቤት…፡፡ከዛ በሶስተኛ አመት የጋብቻ በአላቸው አካባቢ እኔ ተወለድኩ..ወንድ ልጄ ከነቃጭሉ …፡፡አቤት እግዜር ሲመርቅ ተባለ፡፡ተደገሰ፤ተጨፈረ፡፡…ግን ቀናቶች እየገፉ ሲመጡ ሁኔታዬ ግራ እያጋባ መጣ፡፡እንደ መወራጨት እና መነጫነጭ የመሳሰሉት የልጅ ባህሪዎች ከእኔ ዘንድ ሊታዬ አልቻሉም፡፡ሀኪም ቤት ወሰዱኝ፡፡….አስመረመሩኝ
፤ለውጥ የለም፡፡..ለውጥ ብቻ ሳይሆን ይሄ ነው በሽታው የሚል በእርግጠኝነት የሚናገር ሀኪም ጠፋ፡፡አንድ የነርብ ችግር ነው ይላል፤ሌላው አዕምሮው መልዕክት ሰለማይቀበል ነው ይላል፤ቀስ በቀስ ደስታ ያረበበበት የነበረው ቤተሰብ ሀዘን ይጎበኘው ሲጀምር በፈገግታ ብቻ ተውጦ የኖረው ቤተሰብ የተጨማደደ ፊት ማሳየት ጀመረ፡፡
….ቢሆንም ከአመት ከስምንት ወር ቡኃላ ሌላ ልጅ ተወለደ.. ማሀሪ ፡፡ይሄ በመጠኑ መደበታቸውን ጋብ ቢያደርገውም ብዙም አልዘለቀ…በእኔ ላይ ምንም ለውጥ ባለመታየቱ ጭቅጭቁ እንደአዲስ ተጀመረ፡፡መላ አካሌ በድን ነበር..ብቸኛ መንቀሳቀስ ሚችሉት አይኖቼን ብቻ ነበሩ፡፡ከዛ ወዳጅ ዘመድ ነን ባይ ጭራሽ ለወላጆቼ እዚህ ውሰዱት እዚህ ወሰዱት እያለ ድንግርግራቸውን ያወጧቸው ጀመር፡፡…ጠበል ውሰዱት፣አዋቂ ቤት ውስዱት፤እከሌ ሚባል ሀኪም ቤት ውሰዱት….በመጠየቅ ሰበብ እቤታችን ጓራ ያለውን አስተያየት ይሰጥ ነበር፡፡ ወላጆቼም ከእምነታቸውም እየተጋጪ የእኔን መዳን ብቻ ተስፋ በማድረግ ብዙ ነገር ሞከሩ፡፡…ጉልበታቸውን፤ ጊዜያቸውንም፤ ገንዘባቸውንም በተኑ ፡፡ እኔ እንደሆነ ቅንጣት የተባለች ለውጥ እንኳን ማምጣት አልቻልኩም..እኔን ለማስታመም እና ለመንከባከብ ስትል እናቴ ስራዋን ለቀቀችና በአባቴ ገቢ ብቻ መተዳደር ጀመርን፡፡..ሰውነቴ በድን በሆንኩበት እያደገ እና እየተመዘዘ መጣ፡፡ከእኔ ኃላ የተወለደው ወንድሜ መሀሪ ቀድሞኝ መራመድና መናገር ጀመረ፡፡ አራት አመት ሞላኝ፡፡ምንም ለውጥ የለም..የምፈልገውን መጠየቅ አልችል፤ምጸዳዳው በራሴ ላይ፤ምግብ የምበላው በእናቴ እጅ፤ለዛውም በጣም የራሰ እና ለፈሳሽነት የቀረበ ምግብ ሆኖ በግድ በአንድ እጆ አፌን እየፈለቀቀች በእንድ እጇ ምግቡን ወደአፌ በመሰግሰግ፡፡
…ውሀም ሆነ ወተት..ቀና አድርጋ አንገቴን ደረቷ ላይ አስደግፋ አንድ እጇን እንደኩሬ አጎድጉዳ ከታችኛው ከንፈሬ ላይ በመደቀን ወተቱን ወይም ውሀውን እዛ መዳፌ ላይ በማንጮረር በመጋት ነበር ምትመግበኝ…፡፡
አምስተኛ አመት ላይ ስደርስ ግን አባቴ ተስፋ ቆረጠብኝ፤መነጫነጩ ጫፍ ደረሰ፡፡…ከእናቴ ጋር ንትርክ፤ጠጥቶ መግባት፤በአሽሙር መሳደብ ጀመረ…፡፡እናቴም ሰምቶ እንዳልሰማ ማሰለፍ፤ ሲብስባት ማልቀስ የእየእለት ድርጊቷ ነበር ፡፡ቡኃላ ግን ነገሮች በመሻሻል ፋንታ እየባሱ መጡ…የአባቴ ፀባይ እየከፋበት ሄደ፤ውጭ ማድርና ለእናቴ የሚሰጣት የወር ወጪም እየቀነሰ መጣ..በስተመጨረሻ ለእናቴ አስደንጋጭ ምርጫ አቀረበላት‹‹…ከእኔ ወይ ከልጅሽ አንዳችንን ምረጪ››.......

💫ይቀጥላል💫

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot በኩል አድርሱን
👍111
#ዝናባማ_ምሽት

ደጁ ረጥቦ በ'ምባ~ሰማይ ባለቀሰው
በጎዳናው ማዕዘን~አይሄድም አንድ ሰው
ውዴ እኔና አንች~በከተማው መሀል ብዙ መንገድ አልፈን
ከመንገድ መብራቶች~አንዱን ተደግፈን
ተቃቅፈን በካፊያ~ፍቅርን የሞቅንበት ያ ጣፋጭ ውብ ማታ
ትዝ ይለኛል ሁሌም~ምሽቱን አስታኮ የዘነበ ለታ
ዝናባማው ሌሊት~አንች የሌለሽበት
አስተክዞኝ በሀሳብ~ይዞኝ ሄዶ ድንገት
ደጅ የጣለው ዝናብ~ቤቴ ሆኜ አራሰኝ
ያለፈው ትዝታ~አንችን ሲያስታውሰኝ
የምጠለልበት ናፈ'ኩት ገላሽን
ቀላቅሎ ጣለና ዝናብ ትዝታሽን
አስታውሳለው......................................
መሬቱ ርጥብ ነበር ጎርፍ ይንቦጫረቃል
አልፎ አልፎ ይሰማል የሚያስፈራ መብረቅ
በመስመር ብልጭታ ሰማይ ሲሰነጠቅ
በውሀ ነጠብጣብ መሬት ስትደለቅ
ዝናቡን ሊጠለል ሰው ገብቶ ከቤቱ
ከሰው ልንጠለል ከደጅ ወጥተን እኛ
ፍቅርን የሞቅንበት ያ ጣፋጭ ውብ ማታ
ትዝ ይለኛል ሁሌም ሌሊቱን አስታኮ የዘነበ ለታ
አስታውሳለው..........................................
ካፊያው እየጣለ ብርዱ ሲበረታ
ልሞቀው ስጠጋ ፍሙ ከንፈርሽን
በውሀ ነጠብጣብ ውስጥ
ድንገት ብቅ ብሎ ያየሁት መልክሽን
መቸም አልረሳውም......................
በየወቅት ይመጣል ሌላ ክረምት ሆኖ
ትኩስ ጉም ትንፋሽሽ በትዝታ ዳምኖ
ድቅን ይላል ፊቴ~~~ድንግጥ ይላል ልቤ ሁሌም በትዝታ
ምሽቱን አስታኮ የዘነበ ለታ

🔘ቴዲ አፍሮ🔘
👍2
#ሀርሜ_ኮ
:
ክፍል-3

:
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

....‹‹ያን የመሰለ ደስተኛ ኑሮችን እንዲህ ምስቅልቅሉ የወጣው…ይሄ ልጅ ከተወለደ ቡኃላ ነው››
‹‹አረ ተው ጡር አትናገር….ምንም ቢሆን ልጃችን አይደል››አለችው ኮስተር እና ቆፍጠን ብላ..
‹‹አይ ይሄ ልጃችን አይደለም….ይሄ ሳቃችንን የነጠቀን እና ፈገግታችንን የሰረቀን ለቤታችን የተላከ መቅሰፍት ነው››
‹‹ልጄንማ እንዲህ እንድትለው አልፈቅድልህም…..››
ቁጣዋን ችላ ብሎ ሌላ ጥያቄ ጠየቃት ‹‹ታፈቅሪኛለሽ አይደል.?››
‹‹ምን የሚሉት ጥያቄ ነው ….?በደንብ አፈቅርሀለው››መለሰችለት፡፡
‹‹እንደዱሮችን በሳቅ በተሞላ ኑሮ በደስታ እየቧረቅን ልጆቻችንን አብረን እንድናሳድግ ትፈልጊያለሽ አይደል.?››
‹‹አዎ እፈልጋለው..በጣም እፈልጋለው››የተቋጠረ ፊቷን አላቀ የተከደነ ጥርሷን ከፈት አድርጋ በተስፋ መለሰችለት
‹‹እንግዲያው ለእሱም ለእኛም ስንል..ይሄንን ልጅ ለእርዳታ ድርጅት እናስረክበው..እዛ የተሸለ ህክምና ያገኛል..ከእኛ በተሻለ…..››የእናቴ ተስፋ መልሶ ጨለመ...እሱ ለተናገረው እሷ ተሳቀቀች
‹‹እንዳትጨርሰው….ልጄን በህይወት እያለው ለማንም አልሰጥም..እንኳን ለእርዳታ ድርጅት ለገዛ እናቴም አልሰጥ..እንደው አቅም አንሶኝ ለማሳደግ ብቸገር እንኳን ሌሎቹን ልጆቼን አሳዳጊ ልሰጥ እችል ይሆናል እንጂ እሱን አላደርገውም፡፡ምክንያቱም ማንም እንደእኔ ሊረዳው አይችልም..፡፡ ማንም እንደእኔ ሊንከባከበው አይችልም..፡፡ለእኔ ከእግዜር የተሰጠኝ የህይወት ዘመን ፀጋዬ ነው፡፡አንድም ቀን መከራዬ ሆኖ ተሰምቶኝ አያውቅም..ለዛም ነው ፀጋዬ ብዬ የምጠራው››
‹‹እኔ ግን አልችልም..አካሉም አዕምሮውም በድን የሆነ ልጅ ጥዋት ማታ እያየውና እየተሳቀቅኩ ቀሪ ዘመኔን መቀጠል አልችልም…..ያቅማችንን ሞክረናል..ያለንን ገንዘብ ጌጣችንን እና ንብረታችንን ሁሉ እሱን ደህና ለማድረግ ስንል በትነናል…. ከዛም አልፎ እዳ ውስጥ ገብተናል..እንደዛም ሆኖ ግን ምንም ጠብ ያለ ነገር የለም…አዕምሮው የተበላሸ ልጅ ምንም ልናደርገው አንችልም……››
‹‹የእኔ ልጅ አካሉ የማይንቀሳቀስ ሊሆን ይችላል…አዕምሮው ግን ጤነኛ ከሆኑት ልጆችህ በተሸለ ያስባል…. ይሰራል››
‹‹እሱ የእናትነት ልብሽ የሚያስበው ነው…ምኞት፡፡አዕምሮውም ልክ እንደመላ አካሉ አንድ ቦታ ረግቶ የተቀመጠ መስራት ያቆመ..በቃ ምን ልበልሽ… የነከሰ ሞተር ማለት ነው፡፡››
‹‹ተሳስተሀል››እየተንዘረዘረች፡፡
‹‹አልተሳሳትኩም…ያልኩሽን እንድርጊና የቀድሞ ህይወታችንን እንኑር ..አንቺም ወደስራሽ ተመለሺ..የቻልነውን ሞክረናል..እግዜሩም ሰውም በዚህ ውሳኔችን ይደግፉናል እንጂ የሚያዝንብን የለም››
‹‹አልችልም ..በህይወት እያለው.ከልጄ መነጠል አልችልም››
‹‹እንግዲያው የሶስት ቀን ማሰቢያ ጊዜ ሰጥሻለው …እሱ ባለበት እንዲህ በሀዘን የተጨመላለቀ አሳቃቂ ኑሮ ውስጥ መኖር አልችልንም›› ብሎ ፈታኝ ጥያቄ ላይ ጥሏት ወደ ስራ ይሄዳል
እናቴ ለአንድ ቀን ሙሉ በነገሩ ላይ አሰበችበት..አወጣች አወረደች ይሻላል ያለችውን በሁለተኛው ቀን ወሰነች…ወደትምህርት ሚኒስቴር ሄደችና ወደስራዋ አንዲመልሳት ማመልከቻዋን አስገባች..ልጄን ቢያምብኝ ብላ ለክፉ ቀን ያስቀመጠቻትን ሽርፍራፊ ገንዘብ አውጥታ ቤት ተከራየች..በሶስተኛው ቀን አባቴ ስራ ሲሄድ ጠብቃ….አንዳንድ ወሳኝ የሆኑ የእኔን እና የእሷን እቃዎች..መተኛ አልጋችንን..ማብሰያ ዕቃዎችን የመሳሰሉትን አዲስ ወደ ተከራየችው ቤት አጋዘች..ተክሲ ተኮናትራ እኔን ይዛ እቤቱንም ልጆቾንም ጥላ ወጣች….
አንደተለመደው አባቴ አምሽቶ እና ወሳስዶ እቤት ሲመጣ ሶስቱ ልጆች በግራ በመጋባት እና በፍራቻ ውስጥ ሆነው ጎን ለጎን ተኮልኩለው ነበር ያገኛቸው፡፡
‹‹ምን ሆናችሁ.?››
‹‹እማዬ››ከመንታዎቹ አንዷ
‹‹እማዬ ምን.?››
‹‹ሄደች››
‹‹ሄደች ማለት.?››
‹‹ሄደች …ጥላን ፀግሽን በታክሲ ይዛው ሔደች››ግራ ተጋባ
‹‹አመመው እንዴ...?ሀኪም ቤት ነው የወሰደችው.?››
‹‹አይ አይደለም… ይሄን ስጡት ብላለች››ብለው ወረቀቱን አቀበሉት… ገለበጠው፡፡ ለእሱ የተጻፈ ደብዳቤ ነበር፡፡በቆመበት በሚንቀጠቀጥ እጅ ጨምድዶ ይዞ በሚርገበገቡ አይኖቹ ማነበቡን ቀጠለ፡፡
……..ይህቺ ቀን ትመጣለች ብዬ መቼም አስቤ አላውቅም ነበር፡፡ካየውህና ካወቅኩህ ቀን ጀምሮ አፈቅርህ ነበር ..እርግጥ አሁንም አፈቅርሀለው ….. የመጀመሪያ ፍቅሬ ነህ..ሴት ያደረግከኝ አንተ ነህ…ልቤ ካንተ ውጭ ሌላ ሰው ለሽርፍራፊ ሰከንዶች ቢሆን እንኳን ጎራ ብሎበት አያውቅም..ሳገባህ ገነት የገባው አይነት ስሜት ተሰምቶኝ ነበር…አብሬህ ስኖር በሙሉ ልቤና ነፍሴም ጭምር ነበር..፡፡እመነኝ ከአንተ ጋር ህይወቴን ሙሉ ለመኖር ህይወቴንም ቢሆን በክፍያ ለማቅረብ ዝግጁ ነኝ… ልጅን ግን አላደርገውም፡፡ለወደፊትህም አንድ ምክር ልስጥህ አንድን እናት በምንም አይነት ከልጅሽ አስበልጪኝ የሚል ፈታኝ ምርጫ አታቅርብላት ከዛ ይልቅ ሙቺልኝ ብትላት የተሻለ ትክክለኛ እና ፍትሀዊ ጥያቄ ይሆናል…ካፈቀረችህ ያለማቅማማት ልትሞትልህ ትችላለች ..ልጆን ግን…..በፍፅም፡፡
እርግጥ ይገባኛል..ለአንተም ልጅህ እንደመሆኑ መጠን ጫናው ከብዶህ እንጂ ጠልተሀው እንዳልሆነ አውቃለው..እኔ ግን እናት ነኝ መቼም መቼም ቢሆን በልጄ ተስፋ ልቆርጥ አልችልም…ይሄንን ስሜቴን ምን አልባት እመብርሀንም ልጅ ስለነበራት ትረዳኝ ይሆናል..ለእናንተ ስል ልጄን ከምተው ..ለልጄ ስል ሁላችሁንም ባሌንም… ልጆቼንም…ቤቴን ብተው እመርጣለው….እዚህ ላይ ንፅፅር እንዳታደርግ ..ጥለሻቸውስ የሄድሽው ልጆችሽ አይደሉም ወይ ብለህ እንዳትጠይቀኝ..፡፡ከሶስት ጤነኛ ልጆች እንዴት አንድ መላ አካሉን ማዘዝ የማይችል ልጅ ልትመርጪ ቻልሽ እንዳትለኝ...? የዚህን መልስ ለመመለስ ለእኔ ቀላል አይደለም…ግን ቢያንስ እነሱን ማንም ተቀብሎ ሊያሳድጋቸው ይችላል…..የፈለጉትን መጠየቅ የተበደሉትን መናገር ይችላሉ፡፡እቤት ከአንዱ ክፍል እሳት ቢነሳ በጎሮ በር ወይም በመስኮት ዘለው ለማምለጥ ለእነሱ ቀላል ነው፡፡ቢርባቸው እንኳን ማድቤት ገብተው ምግብ ፈልገው ለመጉረስ አይሰንፉም፡፡ሽንታቸውን ቢወጥራቸው ወደ ሽንት ቤት ሄደው ለመሽናት ውሃ ቢጠማቸው ወደ ፍሪጅ ሄደው አልያም ከቧንቧ ቀድተው ደቅነው ለመጠጣት ለእነሱ በጣም ቀላል ነው….አየህ የእኔ ሚስኪን ልጅ ግን ይሄን ሁኑ ማድረግ አይችልም…ምን እንደፈለገ እንኳን መናገር ስለማይችል ከእኔ ከእናቱ ውጭ ማንም ሊረዳው አይችልም…ግን ደግሞ እሱም እንደእነሱ በህይወት አለ..እሱም እንደነሱ ይራባል…፤እሱም እንደነሱ መጸዳዳት አለበት.ያን ሁሉ ማድረግ የሚችለው ግን በእኔ በእናቱ እርዳታ ነው እናም እኔ ለእናንተ ከማስፈልገው በላይ በብዙ ሺ እጥፍ ለእሱ አስፈልገዋለው ስለዚህ አንተንም ላለመረበሽ ስል ቤቱን ለቅቄ ልጄን ይዤ ወጥቼያለው፡፡አይዞህ እንዴት ይኖራሉ ብለህ አታስብ ወደ ስራዬ ለመመለስ ስለወሰንኩ ማመልከቻ አስገብቼያለው አንተም ልጆችህን ጥሩ አባት ሆነህ እንደምታሳድግ ምራጫውን ለአንተ ትቼዋለው ከፈለግክ ሰራተኛ ቅጠር …ከፈለክም ማግባት ትችላልህ፡፡ በዚህ ምንም ቅሬታ አይሰማኝም…..ፍቺያችንንም ዝግጁ ስትሆን ንገረኝና በአጭር ቀናት ውስጥ እንዲያልቅ አደርጋለው፡፡ብቻ አደራ ምልህ እቅፍ ውስጥ ላሉት ሶስት ጤነኛ ልጆቸች ጥሩ አባት ሁናቸው፡፡ያንተው አክባሪህ
ፈጽሞ ያልጠበቀው ዱብ እዳ ነው ያጋጠመው..መቼም እንዲህ አይት ውሳኔ ላይ ትደርሳለች ቡሎ ገምቶም ጠርጥሮም አያውቅ ነበር .፡፡በእሱ የምትጨክን
👍6🔥1🥰1
በልጆቾ የምትጨክን….ከዛ ቡኃላ አባቴ እኔን መራገም ጀመረ… የበለጠ ጠላኝ….….ከእናቴ ጋር እልክ ተጋባ..‹‹ልጇን ትቻል..ልጆቼን ችላለው››በማለት ፎከረ ‹‹ላም ቀንዶ አይከብዳትም››አለ..በማግስቱ በሰው በሰው አፈላልጎ ለቤቱ ሰራተኛ ቀጠረ…ከእናቴ ጋር አንድ ትምህርት ቤት ስለሚስተምሩ በእየእለቱ ቢገናኙም አይነጋገሩም ነበር.. አንድ ወር አለፈ… የወዳጅ ዘመድ ጉትጎታ እና አማላጅነትም ፍሬ ስለላፈራ በሁለተኛዋ ወር ፍቼ ፈጻሙ….በተጋቡ በስምንት ዓመታቸው ማለት ነው ….ሰማኒያቸው ተቀዳደደ… በቃ.
…..በሶስተኛው ወሩ ለእናቴ ከአባቴ ደብዳቤ ደረሳት……
ሁሉ ነገር ህልም ነው የሆነብኝ..እንዴት ገነት ውስጥ እንዲህ በድንገት ሲኦል ሊመሰረት ይችላል...?እንዴት ያ ሁሉ በመካከላችን የነበረው ሳቅና ፈንጠዝያ ወደ ሀዘንና መሳቀቅ ሊቀየር ቻለ….?ምን አይነት መቅሰፍት ነው በትዳራችን ላይ የዘነበው….?ምን አይነት የእዮብን አይነት ፈተና ነው ለቤተሰባችን የተላከው….?የእዬብን አይነት ፈተና እኮ በድል ለመወጣት ከእዬብን አይነት ትዕግስት ጋር አብሮ መፈጠርን ይጠይቃል፡፡ታውቂያለሽ እኔ ደግሞ እንደዛ አይነት ሰው አይደለውም..ያ ላንቺ የተሰጠ ስጦታ ነው..መቼስ ይገባሻል ማንም ሰው የገዛ ልጁን አይጠየፍም..እኔ ግን አልቻልኩም ፡፡
እሱን እያየው መሳቀቁ ካቅሜ በላይ ነበር….፡፡እና ልገላገላው እንደምችል ማሰብ ጀመርኩ፡፡ ላንቺ እንደዛ አይነት ምርጫ ሳቀርብልሽ ብታንገራግሪም የምትቀበይኝ መስሎኝ ነበር..ግን የጽናትሽን መጠን አላውቀውም ኖሮል…እንኳንም ጥለሺኝ ወጣሽ…እንኳንም ፈታሺኝ..እኔ ለአንቺ የምገባ ሰው አይደለውም..ለአንቺ ባልነትም የሚመጥን ስብዕናና ያለኝ ግለሰብ አይደለውም…፡፡ለልጆቼ አባት… ለተማሪዎቼ አስተማሪ ….ለአንቺም ባል.. ሆኜ ለመቀጠል ሞራሉ የሌለኝ ከንቱ ሰው ነኝ….፡፡የገዛ ልጁን የተጠየፈ ሰው እንዴት የሰውን ልጅ ተከታትሎ እና ተንከባክቦ በማስተማር የሀገርን አደራ ተቀብሎ መልካምና ውጤታማ ዜጋ ሊያፈራ ይችላል…በፍፅም..ጥሩ አባት መሆን ያልቻለ ሰው ጥሩ መምህር ነኝ ቢል ምፀት ነው… ስለዚህ ከአሁን ቡኃላ ለፀጋ ብቻ ሳይሆን እኔጋ ላሉ ሶስቱ ልጆቻችንም ከእኔ ይልቅ አንቺ ነሽ ምታስፈልጊያቸው…አንቺ እቤቱን ለቀሽ ከወጣሽ ቡኃላ አንድ ቅጽበት እንኳን በፊታቸው ላይ ሳቅ ልፈጥር አልተቻለኝም…..፡፡
ቤቱ ሬሳ የወጣበት የሙት መንፈሶች ጉባኡ የተቀመጡበት መቃብር ቤት ይመስላል….ስለዚህ ስራዬን ትቼ ልጆቼን ትቼ… ሀገሩን ለቅቄ ሄጄያለው..ወዴት ብለሽ እንዳትጠይቂኝ…ልታፈላልጊኝም እንዳትሞክሪ .. ለጊዜው መሄዴን ብቻ እንጂ ወዴት እንደምሄድ እኔም እራሴ አላውቀውም…..ብቻ በመጨረሻ አንድ ነገር ላስቸግርሽ..እውነት እንደምታምኚው የልጅሽ አዕምሮ በትክክል ጤነኛና የሚያገናዝብ ከሆነ እኔ አባቱ ያደረኩበትን ነገር ነግረሽ ግን ደግሞ ከቻለ ይቅር እንዲለኝም ጠይቂልኝ….››
በይ ቻው ያንቺው አፍቃሪ….
እናቴ ደብዳቤውን በእንባ እየታጠበች ነው ያነበበችው..ውስጥ ድረስ በጠሊቅ የሚጠዘጥዝ እና አጥንት የሚያሳሳ ሀዘን ነበር ያጋጠማት …እርግጥ እቤቱን ጥላ የወጣች ቀን ከፍቷት ነበር …ግን በዚህ መጠን አልነበረም ..፡፡ሰማኒያቸውን ፍርድ ቤት ቀርበው የቀደዱ ቀንም ከፍቷት ነበር ግን እንደዚህ ቅስሞ አልተሰበረም ነበር
በስተመጨረሻ እናቴ ምርጫ አልነበራትምና …መኪና ፈልጋ እቃዎቾን ጭና እናም እኔንም ተሸክማ ወደ ቤቷ ተመልሳ ገባች… ከልጆቾ ተቀላቀለች…፡፡
ይሄው እቤቱም አሁን ያለንበት ነው … ልጆቹም እኔንም ጨምረው ጓረምሰው እዚሁ ቤት አሉ …አባቴ ግን…. አባቴ በአሁኑ ጊዜ የት እንዳለ ሌላ ጊዜ እነግራችሆለው..፡፡እናቴ ግን በአስተማሪ ደሞዞ እኛን አራት ልጆቾን አንቀባራ በስርአት አስድጋናለች ፡፡ደረጃው ይለያይ እንጂ ሁላችንንም አስተምራናለች.. ይሄው እስከአሁንም ከእሷ ትከሻ ላይ ሁላችንም ሙሉ በሙሉ አልተላቀቅንም..ታዲያ ሀርሜ-ኮ ጀግና አይደለች….ታዲያ የልቤ የክብር ሊሻን አይገባትም ትላላችሁ....እናቴ ለእኔ ገነቴ ነች፡፡
በነገራችን ላይ እናት ብቻ ሳትሆን ሀገርም እንዲሁ ነች፡፡ሀገር በጦርነት ወይም በአመፅ ስትታመስ የምትጨነቀውና በተራሮቾ ላይ ሸሽጋ፤ በዋሻዎቾ ውስጥ ሸጉጣ ፤በጫካዎቾ ውስጥ ሰውራ ህይወታቸውን ማተረፍና የተሸለ ቀን እስኪመጣ ለማቆየት የምትጥረው ባላገሮች የሆኑትን ጎስቆላዎችን እና ሚስኪን ዜጎቾን ነው፡፡ሀብታሞቹና የነቁት ምሁራኖችማ እራሳቸውን ለማዳን ሁሌ ዝግጁ ናቸው፡፡ገና የመጀመሪያውን የጥይት ተኩስ ሲሰሙ ብራቸውን ሰብስበው፤ ሻንጣቸውን ሸክፈው ፓስፖርታቸውን ይዘው በቦሌ በኩል እብስ ነው፡፡ከዛ አነስ ያለውም በሞያሌና በመተማ ቀሪው በጅብቲ በኩል ይነጉድና ከእሳቱ እርቆ ከመከራው ተጠብቆ የተሸለ ቀን እስኪመጣ እራሱን በምቾት ያቆያል፡፡እና ሀገር በመከራ ጊዜ የምትጨነቀው በፍፅምነትም የምታስፈልገው ወደየትም ጥጋት መሸሻ ሀሳቡም እድሉም ለሌላቸው ሚስኪን ዜጎቾ ነው…ልክ እንደ እናት፡፡

💫ይቀጥላል💫

ይህን የእናትነትን ፅኑ ፍቅር ውስጡ የገባ አንብባችሁ ስትጨርሱ 👍 እያረጋችሁ እለፉ አብሮነታችሁንም በዛው እናያለን

አስተያየታችሁንም @atronosebot አድርሱን
👍31🔥1
#ሀርሜ_ኮ
:
ክፍል-አራት

:
:
ደራሲ.ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

...እቤት ውስጥ ማንም የለም …..እኔ ሳሎን ሶፋው ላይ ተመቻችቼ ተሰትሬ ተኝቼያለው…አንገቴ ከፍ የሚያደርግ ልዩ አይነት ትራስ ከስር ተደርጎልኝ ቀና ብያለው…ፊት ለሰፊቴ ግድግዳ ላይ ለእኔ እይታ እንዲመች ተስተካክሎ የተለጠፈ 32” ሶኔ ፍላት ቴሌቬዝን ላይ አፍጥጬ…. ‹‹ብሬኪንግ ባድ›› የሚል ርዕስ ያለው ተከታታይ ፊልም እያየው ነው…፡፡ያው ከመጽሀፍ ቀጥሎ ፊልም ማየት በጣም የምወደው እና የሚያዝናናኝ የእየ እለት ድርጊቴ ነው..
ስለአለም ያለኝን ግንዛቤ በጣም ያሰፋልኝ የማያቸው የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ፊልሞች ናቸው..፡፡በቀን ቢያንስ 5 ፊልም አያለው..ቢያንስ ነው..እሰከ አስር እና ከዛም በላይ የማይበት ቀን አለ…፡፡ከሁሉም በላይ ግን በእናቴ እና አልፎ አልፎ በወንድሜ የሚነበብልኝ መጽሀፍት ለእኔ ሱሴ ናቸው..
በዚህ ውስብስብ የህይወት ቆይታዬ የተረዳውት አንድ ዋና ፌሬ ነገር ቢኖር መጻሀፍን የሚተካ ምንም ነገር አለመኖሩን ነው…ፊልም፤ኢንተርኔት ምንም ቢሆን ምንም፡፡ መጽሀፍ አዕምሮን እንደሚያዳብር አምናለው….ማንበብ የማሰብ ብቃትን የሚያጠነክር የአእምሮ ስፖርት ነው፡፡መፅሀፍ ስናነብ ቃሉን ወደ አዕምሮችን ልከን ምስሉንና እያንዳንዱን ድርጊት በራሳችን የአዕምሮ ግንዛቤ እና ፍላጎት መጠን አስልተን በራሳችን ዳሬክተርነት አክረተሮችን በምናባችን ፈጥረን ፊልሙን በመስራት የታሪኩን ሙሉ ጭብጥ ለመረዳ እንጥራለን፡፡ይሄ ሁሉ ውጣ ውረድ ታዲያ የማሰብ ብቃታችንን በጊዜ ሂደት ውስጥ ሚያፈረጥምልን የአዕምሮ ቅልጥፍና ማበልፀጊያ ጅምናስቲክ ማለት ነው…..፡፡
ለማንኛውም ሰው ካረዳኝ በራሴ መጽሀፍ ማንበቡ ስለሚከብደኝ አሁን ፊልሙን እያየው ነው እንዲህ አሁን ባለውበት ሁኔታ ሁሉን ነገር አስተካክላልኝ የሄደችው እናቴ ነች…ቤቱ ባዶ ከሆነ ሁለት ሰዓት በላይ ሆኖታል.የቤታችን ተንከባካቢ ትርሲትም እንኳን አስቤዛ ልትሸምት ወደ መርካቶ ከሄደች ቆየች…
አሁን ግን በሩ ሲከፈት ሰማው…ማን እንደሆነ አንገቴን ጠምዝዤ በአይኖቼ ማየት አልችልም…፡፡
ግን በበር አከፋፈቱ እና በእርምጃው ማንነቱን ወዴያው ነው ያወቅኩት…ወንድሜ መሀሪ ነው፡፡አዎ መጥቶ ፊት ለፊቴ ተገተረ..ያው እንደወትሮው ጭብርር እንዳለ ነው….በጥቁር ፔስታል የታጨቀ ዕቃ ተሸክሞ በመምጣት አጠገቤ ካለው ጠረጵዛ ላይ ጎንበስ ብሎ አስቀመጠውና እሱም አጠገቤ ቁጭ በማለት
‹‹ሀይ ወንድሜ?›› አለኝ እንደሁልጊዜው አይኖቼን በማርገብገብ ለሰላምታው ምላሽ ሰጠውት
‹‹ማንም የለም እንዴ?››የግራ እጄን የማሀል ጣት በማወዛወዝ ቤቱ ባዶ እንደሆነ ነገርኩት ፡፡እጁን ወደ ፔስታሉ ሰደደና በፕላስቲክ የታሸገ የመንጎ ጭማቂ አወጣ…ከፈተውና እስትሮ አደረገበት..ከዛ ወደ እኔ አፍ አስጠጋና ጭማቂውን በግራ እጁ ይዞ በቀኝ እጁ እስትሮውን አፌላይ ሰካው ‹‹…በል እንግዲህ እድሜ ለወንድሜ እያልክ ምጠጥ ››አለና ከእስትሮው በተነሳ እጁ ሪሞቱን በማንሳት እያየውት የነበረውን ፊልም ዘጋው‹‹ይቅርታ…አሁን ፊልም ማየት አትችልም …ወይ መጽሀፍ እናነባለን ..ወይም እናወራለን›› አለኝ
ፈገግ አልኩና በሀሳቡ እንደተስማማው ገለጽኩልት..ግማሽ ሊትር የሆነችውን ጅውስ ለመጠጣት ግማሽ ሰዓት ያህል ፈጀበኝ…ያን ሁሉ ጊዜ ወንድሜ ያለምንም መቻኮልና መሰልቸት በቀልድ እያዋዛ ነበር ጅውሱን የመገበኝ፡፡
‹‹በል እንግዲህ አሁን ደግሞ ያራሴን ጅውስ ልጠጣ›› አለና እኔ የጠጣውበትን ባዶ የጅውስ ፕላስቲክ ወርውሮ እጅን ወደ ፔስታሉ ከተተና በለጬ ጫቱን መዞ በማውጣት ጠረጵዛው ላይ አስቀመጠው…አሁንም እጁን በድጋሜ ሰደደና የፕላስቲክ እሽግ ኮካና በወረቀት የታሸገ ለውዝ አውጥቶ እዛው ጠረጵዛ ላይ በመደዳ ደረደራቸው፤ የጫቱን ፔስታል ከፍቶ የጫቱን እስር ፈቶ አንድ ሁለት ቅጠል አወጣና በቄንጥና በፍቅር እየቀነጣጠሰ ወደ አፉ በመውሰድ ይጠቀጥቀው ጀመር…ከዛ ኮካውን ከፈተና ተጎነጨለትና መልሶ አስቀመጠው…ሌላ ጫት መዘዘ ቀነጠሰና ጎረሰው…ለውዙን ፈለፈለእና ወደ አፉ ጨመረ…….ከዛ ከለበሰው ግብዴ ጃኬት ሰፊ ኪስ ውስጥ መፃፍና አወጣና ገለጦ ማንበብ ጀመረ..ሁሌ እስኪግል እንዲህ ነው የሚያደርገው…ለሀያ ደቂቃ ያህል በፅሞና ካነበበ ብኃላ አጣጥፎ አስቀመጠውና ወደ እኔ ዞረ.
‹‹አንድ ነገር ላውራህ እስኪ›› ሲል ጀመረ..ለመስማት ተዘገጀው…ያው ተዘጋጀው ስል ስሜቴን አነቀቃው ማለቴ ነው…ታናሽ ወንድሜ ቀጠለ ‹‹ምን አልባት የምትወደውን ወሬ ላይሆን ይችላል ላወራልህ የተዘጋጀውት..ግን ይሄንን ወሬ ካንተ ጋር ካልሆነ ከሌላ ከማንም ሰው ጋር ላወራው አልችልም..ከእህቶቼም ጋር.. ከእናቴም ጋር..፡፡ለምን? ብትለኝ እኔ እንጃ ነው መልሴ….፡፡ ከእነሱ ጋር ማውራት ከአንተ ጋር እንደማውራ አይቀለኝም..፡፡ምን አልባት አንተ ጥሩ አድማጭ ስለሆንክ ሊሆን ይችላል..ምን አልባት ሁለታችንም ወንድም አማቾች ብቻ ሳንሆን የቤቱም ብቸኛ ወንዶች ስለሆን ሊሆን ይችላል….››አለና ንግግሩን አቆርጦ ፔስታሉን ወደ ራሱ ጎተት አደረገና ጫቱን ከውስጡ መዝዞ ቀነጣጥሶ በመጉረስ በላዩ ላይ ኮካ ተጎነጨለትና ጠርሙሱን አስቀምጦ ንግግሩን ካቆመበት ቀጠለ…‹‹ላወራህ የፈለግኩት ስለአባቴ ነው….ማለት ስለአባታችን…ያው ስለእሱ መስማት እንደማትፈልግ እና እንደማትወደው አውቃለው…እኔም ስለእሱ ሳስብ ግራ የሚያጋባ ስሜት ነው የሚሰማኝ….እርግጥ አልዋሽህም አንዳንዴ ምን አለ አጠገቤ ቢኖር ብዬ እመኛለው....እርግጥ ለእዚህ ቤተሰብ መክፈል የሚገባውን መስዋዕትነት አልከፈለም…..ያ ትልቅ ድክመቱ ነው…ግን ያው ምንም ቢሆን አባቴ ነው….ዝም ብዬ እንዳልተፈጠረ ሰው ልቆጥረውና ልረሳው አልችልም …
አሁን ስለእሱ ላወራህ የቻልኩት አንድ ጽሁፉን ፌስ ብክ ገጹ ላይ አንብቤ ነው..ያው እንግሊዝ ከገባ ቡኃላ ሀይለኛ ፖለቲከኛ ሆኗል….፡፡ ስለዲያስፖር ፖለቲካ ደጋግሜ አውርቼሀለው…አባታችን ከነዛ ተዋናዬች ውስጥ ዋናው ሆኗል..ይግርምሀል ስለአባቴ ብዙ ነገሮቸ ለማወቅ ሞክሬያለው..ማለት ያው ጥሎን ሲሄድ ህጻን ስለነበርኩ እንደ ህልም ነው ሚታወሰኝ..ግን እዚህ ሳለ እንዴት አይነት ሰው ነበር…?ምን አይነት አባት…እንዴት አይነት አስተማሪ…?እንደነበር ከተለያ ሰዎች ለማጣራት ሞክሬያለው…፡፡
እዚህ አገር ሳለ የነበረውን የፖለቲካ ተሳትፎም ለማወቅ ጥሬያለው…..እርግጥ እዚህ እያለ የሆነ ፓለቲካ ድርጅት ውስጥ አባል ነበር..ግን ማንም የማየውቀውና እዚህ ግባ የማይባል ተሳትፎ የነበረው ተራ አባል ነበር…. አሁን በገጹ ላይ የሚጽፋቸው ጽሁፎችን ሳነብ ልክ ከዚህ ሀገር የወጣው የፖለቲከኛ ስደተኛ ሆኖ ከኢህአዲግ የእስር መንጋጋ ሾልኮ በሱዳን በኩል ኮብልሎ በስቃይ አሁን ያለበት ሀገር እንደደረሰ ነው፡፡
እኔም አንተም እንደምናውቀው ሀቁ ግን አባታችን የፖለቲካ ስደተኛ ሳይሆን የኑሮ ስደተኛ እንደሆነ ነው…፡፡ያው ታውቀወለህ ለምን ጥሎን እንደሄደ..እሱ ግን በዲያስፖራው አለም ያለውን ተቀባይነት ለማግዘፍ ‹‹…ስራዬን ለቅቄ ቤተሰቤን በትኜ በስደት አለም ከ15 አመት በላይ የእየባከንኩ ያለውት በዘረኛው መንግስት ምክንያት ነው…››ብሎ የጻፈውን አንብቤ ምን አይነት ውሸታም አባት ነው ያለን ?ብዬ ልታዘበው ችያለው…ግን እንደዛም ሆኖ በሆነ ተአምር ወደ ሀገር ተመልሶ ለአንዴም ሰከንድ ቢሆን ፊት ለፊት በአካል ባየው ደስ ይለኛል..ይገርምሀል እኔ ብቻ አልምሰልህ እናቴም በጣም ትናፍቀዋለች..መአት ቀን ፎቶውን በተመስጦ እየተመለከተች እንባዋን ስታንጠባጥብ ደርሼባታለው …ግን እውነቱን ለመናገር የእናቴ እንባ ለእሱ
👍12
አይገባውም….ለምን መሰለህ…
የበር መከፈት ድምጽ ሲሰማ ንግግሩን አንጠልጥሎ ተወው‹‹…ወይ አንተ መጥተሀል….ነፍስ እኮ ነህ…. ፀጋ ብቻውን ይሆናል ብዬ እንዴት ልቤ ተንጠ ልጥሎ ነበር መሰለህ..መቼስ እዚህች ጭንቅንቅ ከተማ ውስጥ እንዳሰቡት ወጥቶ ባሰቡበት ሰዓት ተመልሶ ወደ ቤት መግባት ሱሚ ከሆነ ከራርሞል፡፡››አለች ትርሲት እስከነ ሸክሞ ወደ ውስጥ እየዘለቀች፡፡
እውነትሽን ነው ..ግን ለፀግሽ እኮ ይሄን ያህል መጨነቅ አልነበረብሽም..እሱ ብቻውን በሆነ ሰዓት የትም ልሁን የትም ትከሻዬ ይነግረኛል፡፡እና ያው እንደምታዬው ልክ እንደዛሬው በርሬ ከጎኑ እገኛለው››በማለት ጉራውን ነዛባት..
‹‹እሱስ እውነትህን ነው..ቤተሰቡ ሙሉ እኮ አንተ ጤነኛ አዕምሮ እንዳለህ እና በትክክል እንደምታሰብ በማመን በጥቂቱም ቢሆን እንድንጽናና እና አማኑዔል ወስደን እንዳናስቆልፍብህ ምክንያት የሆነን ብቸኛው ምክንያት ለፀግሽ በምታደርገው እንክብካቤ ብቻ ነው..እንጂማ..!!!
‹‹አንቺ ..!!!››ተስፈንጥሮ ከመቀመጫው ተነሳና ሸምታ የመጣችውን አስቤዛ እንደያዘች ወደሚቀጥላው ክፍል ከመግባቷ በፊት ፊት ለፊቷ ተጋርጦ‹‹ምን አልሽ እስኪ ?ድገሚልኝ››አላት በንዴት
‹‹እወነቴን ነው..!!አንተ እኮ….››
‹‹እኔ አኮ ምን..?››
‹‹ያው…
እስቲ የእነሱን ጭቅጭቅ መስማቱን እናቆርጥናና ስለእዚህች ሚስኪን ትርሲት ላውራችሁ..ከዚህ ከእኛ ቤት ውስጥ ማሀሪን እንደፈለገች የመናገር ስልጣኑም ድፈረቱም ያላት ብቸኛዋ ሰው እሷ ነች…እሱም ዝም ብሎ ዘራፍ ይላል እንጂ በእሷ አይጨክንባትም…ይህቺ ሴት እንደሰራተኛችን መቁጠር ካቆምን ዓመታት አልፈዋል፡፡እሷም እራሷን እንደቤተሰቡ የመጀመሪያ ልጅ ነው ምታስበው፡፡ከሁለት አመት በፊት የሆነውን ነገር ልንገራችሁ…ሳይታስብ ግማሽ እህቷ ከብዙ አመታት የአሜሪካ ቆይታ ቡኃላ ወደ ሀገር ቤት ለእረፍት ትመጣለች፡፡ከትዕርሲት ጋር ይገናኛሉ…ለዲያስፖራዋ ከሞች አባቷ የተገኘች ብቸኛ እህተቷ ስለሆነች በጣም ትጎጎና ጥላት ላለመሄድ ትወስናለች….ዝግጅቱ ይጀመራል… ቤተሰቡ ሁሉ እሷን ለመሸኘት በደስታም ግራ በመጋባትም ሽር ጉድ ይላል…እህቶቼ በእሷ እድል ይቀናሉ….በስተመጨረሻ ሁሉ ነገር ተጠናቆ ለመብረር እንድ ሳምንት ሲቀራት ድንገት‹‹አልሄድም›› አለች..በቃ ግግም ብላ አልሄድም… ሀገር ግራ ተጋባ ..ጤንነቷን ሁሉ የተጠራጠሩ ብዙዎች ነበሩ…እንደእህቴ ሮማን ደግሞ ‹‹አይ አለማወቅ!!›› ብለው ሊያሽሞጥጦት ሞክረው ነበር….
‹‹እንዴት አንድ ጤነኛ ሰው አሜሪካን ከመሰለች ለገነት ከቀረበች የነፃነት እና የብልጽግና ሀገር ይልቅ ኢትጵያን የመሰለች ለሲኦል የቀረበች ችጋር እና የመከራ መፈልፈያ ሀገር ይመርጣል..?››ይሄ ዓረፍተ ነገር ቀጥታ ከእህቴ ከሮማን የወጣ ቢሆንም የብዙዎች ድጋፍና ይሁንታ ያገኘ ነበር
‹‹አንዳንዴ ገነትንም ቢሆን አሳልፈው የሚሰጡለት ሰው አለ›› ፍርጥም ብላ መለሰች ትርሲት
‹‹ያ ሰው ማን ነው?››ሰው ሁሉ ማንነቱንም በአድናቆት ለማወቅ ተራኮተ…በልቧ እንዲህ የነገሰው ድብቁ ሰው ማነው.. ?.ቤተሰቡ ሁሉ ለማወቅ በየፊናው ኢንተርቪው ያደርጓት ጀመር…በሰተ መጨረሻ ነው ማንም የለም ፀግሽን ግን ጥዬ ልሄድ አልችልም ብላ እኔንም ሌሎችንም ያስፈዘዘ መልስ የመለሰችው፡፡
‹‹ምን ማለትሽ ነው››
እሱን ከእናቱ ቀጥሎ የምረዳ እኔ ነኝ..እናቱ ደግሞ ሁሌ 24 ሰዓት አብረው ልትሆን አትችልም ..የሚያግዛት ሰው ያስፈልጋታል፡፡እሱን በእንዲህ አይነት ሁኔታ ጥዬ ብሄድ እግዜሩም መንገዱን ቀና አያደርግልኝም››እህቶቼ ተንጫጩ
‹‹..እንዴ እኛም እኮ አለንለት….?››
‹‹አይ የእናንተ መኖር እንኳን እንዲሁ ለስም ነው…በየፊናችሁ ተበታትናችሁ ውላችሁ ወደ ቤት የምትመለሱት ለመኝታ ነው…››
‹‹እኔ እህቱ እንኳን ብሆን ይሄ እድል ቢገጥመኝ ለእሱ ስል መስዋት አላደርገውም…››ፌናን የምታስበውን ስትደብቅ ተናገረች፡፡
‹‹እኔ እህቱ ስትይ ምን ለማለትሽ ነው …?እኔስ ምኑ ነኝ..?››ተንደርድራ የፌናንን አንገት አነቀች፡፡ከፍተኛ ጩኸት እና ብጥብጥ ተከሰተ..በስንት እግዚዬታ ነገሩ በረደ……ከአሜሪካ ጉዞዋ ግን በዛው ጨክና ቀረች፡፡
ያ ውሳኔዋ ግን ሁሉንም ሰው የተዓምር ያህል ያስደነቀ ድረጊት ነበር..ማንም ሰው እኮ እንደእኔ አይነት ሰውነቱን ማዘዝ የማይችል ሰው ያለበት ቤት ተቀጥሮ ለመኖር እራሱ ፍቃደኛ አይሆንም..ማንም…ምንም ያህል ብር ቢከፈለው..፡፡እሷ ግን ልዩ ነች..፡፡ደሞዝ እንኳን መቀበሏን እርግጠኛ አይደለውም…እናቴ በሌለችበት ጊዜ (አሁን አሁንማ እናቴም እያለች) ሰውነቴን የምታጥበኝ. ልብሴን የምትቀያይርልኝ… እሷ ነች..፡፡ለዛውም በፍቅር ..ያው ሁለተኛዋ እናቴ በሏት…‹ሳይደግስ አይጣላም› የሚባለው እንደዚህ አይደል፡፡

💫ይቀጥላል💫

Like👍 ማድረግ እንዳይረሳ

አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን
👍3
ይኸው ..
ትከሻዬ ሰፍቷል
ጉልበቴ በርትቷል
ክንዴም ቢሆን ሰብቷል
እያልኩኝ ሳቅራራ ፣ ስፎክር ፣ ሳናፋ
ግምባሬ ከምኔው ፣ እግርሽ ስር ተደፋ?
ወይኔ!!
ጀግና እንዳልነበርኩ፣
የአናብስት ግሳት ፣ ማያስደነግጠኝ
የሺህ ሰራዊት ድምፅ ፣ ደንታ የማይሰጠኝ
ዝምታሽ እንደሰም ፣ በቁሜ ያቅልጠኝ?
የባሩዱን ሽታ ስምገው እንደጣን
ጫካውን ስገስፅ፣
ተራራውን ሳዘው ፣ እንደባለስልጣን
ሁሉንም ስገዛ ፣ እግሬ ስር አድርጌ
ቆይ ...በምን ተአምር ነው፣
ራሴን ያገኘሁት ከትዛዝሽ ግርጌ?
አንበሳ ነኝ ብዬ፣
መሬቱን እየጫርኩ ጫካው ላይ ሳገሳ
"አይ 'ቴ ፉከራ አንተን ብሎ አንበሳ"
በሚል ስውር አሽሙር አይተሽኝ አልፈሻል
ከቶ በምን አቅም ከገዳይ ይሸሻል?
ያንችው ነኝ
ያንችው ነኝ ... እወቂው ከንግዲህ
የማን ነኝ እላለሁ?
ኩራቴን በካልቾ ክብሬን በጠረባ ከዘረርሽው ወዲህ!
ሂድ ስትይኝ ልሂድ ና ስትኝኝ ልምጣ
እንደግዞተኛ፣
በትዛዝሽ ልግባ ፣ በትዛዝሽ ልውጣ
ምን አቅም አለኝና፣ ከቶ በምን ወኔ፣ እከራከራለሁ?
በፈለግሽኝ ሰአት፣
በፈለግሽኝ ቦታ፣ እዚያም - እዚም አለሁ!
ጥሪኝ ብቻ!
#ሀርሜ_ኮ
:
ክፍል-አምስት

:
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

...ከልደቴ ከ5 ቀናት ቡኃላ ከምሽቱ 4 ሰዓት አካባቢ ነው፡፡ተኝቼያለው፡፡እንቅ
ልፍ ግን አልወሰደኝም....ቢሆንም ግን አይኖቼ ተጨፍነዋል፡፡እናቴ መኝታ ቤቱን በራፍ ከፍታ ወደ ውስጥ ስትገባ ይሰማኛል‹‹…ወይ ልጄ እንቅልፍ ወሰደህ?›› አለችና ግንባሬን ስማ አልጋው ላይ ስትቀመጥ ይታወቀኛል…ወዲያው ግን ትርሲት‹‹ እቴቴ…እቴቴ›› እያለች ወደውስጥ ስትገባ ሰማዋት…
‹‹ምነው… ?ምን ፈለግሽ..?››
‹‹ፀግሸ ተኛ እንዴ?››
‹‹እዚህ ፊልም ላይ ሲፈዝ ውሎ ደክሞታል መሰለኝ በጊዜ ተኝቷል››
‹‹አይ ጥዋት ቁርስ ምን ልስራልሽ ልልሽ ነው?››
‹‹አይ ..ምንም.. ነገር እኮ አርብ ነው ..ፆም ነው..ቁርስ አልፈልግም››
‹‹ውይ… አይ የእኔ ነገር!! ረስቼው››
‹‹እሺ በይ ደህና እደሪ››
‹‹ደህና እደሪ…ግን ነገ ከትምህርት ቤት እንደመጣው ፀግሽን ይዤ ከከተማ እወጣለው፡፡››
‹‹እወጣለው ስትይ?››
‹‹ልጄን ይዤ ቅዳሜ ና እሁድ ሶደሬ ነው የማሳልፈው››
‹‹መኪና አገኘሽ እንዴ…?››
‹‹ወንድም ጥላ ከሹፌር ጋ ልክልሻለው ብሎኛል›› ወንድም ጥላ የምትለው ታለቅ ወንድሞን ነው….አጎቴን፡፡
‹‹አሪፍ ነዋ..ግን እኔንም ይዛችሁኝ ብትሄዱ አሪፍ ነበር››
‹‹አይ ከልጄ ጋር ለብቻዬ መሆን ነው የምፈልገው››ይሄን ሁሉ ንግግራቸውን አድፍጬ እየሰማዋቸው ነው..፡፡
‹‹በቃ እንደፈለግሽ…ስለዚህ በአንድ ሻንጣ ቅያሬ ልብስ ላዘጋጅላችሁ አይደል?›››
‹‹አዎ ..ፀግሽንም ሰውነቱን አጥበሽ ብትጠብቂኝ ደስ ይለኛል››
‹‹ሰውነቱን!!!››አለች ልክ አዲስ ነገር እንደሰማ ሰው በመደነቅ
‹‹ምነው አዎ ሰውነቱን››
‹‹ግን እኮ እቴቴ…››በሰለለ ድምፅ
‹‹እንዴ !!ሰላምነሽ ግን..?ምነው ችግር አለ?››
‹‹አይ!! እንደው ነግርሻለው እያልኩ…››
‹‹ምኑን ነው የምትነግሪኝ?››
‹‹ማለት ትንሽ ያሳፍራል››
‹‹ኦ ሴትዬ በውድቅት ለሊት አታድርቂኝ…በቃ ማጠቡ ከከበደሽ ተይው እኔ ስመጣ አጥበዋለው››በተከፋ የድምጽ ቀና ተነጫነጨችባት
‹‹አይ እኔማ አጥበዋለው…እሱን መንከባከብ በጣም ደስ እንደሚለኝ ታውቂያለሽ..በጣም የምወደው እና የምሳሳለት ወንድሜ ነው..ግን በቀደም የልደቱ ቀን ሰወነቱን ሳጥበው…››
‹‹ሰውነቱን ስታጥቢው ምን….?››
‹‹ሰውነቱን ሳጥበው እንትኑ ቆመ..ለረጅም ደቂቃ ግትር ብሎ ቆመ ..እንዲህ ሲሆን አይቼው አላውቅም››
‹‹ምኑ ቆመ .. ?ምን ንገሪኝ..?››
‹‹እንዴ እቴቴ ደግሞ…. እንትኑ ነዋ..ለምን ታሳፍሪኛለሽ?››ይሄንን ስሰማ ባደፈጥኩበት ሆኜ እንዴት እንደተሸማቀቅኩ አትጠይቁኝ …በራሴ አስቤበትና አቅጄ የሆነ ወንጀል የሰራው ነው የመሰለኝ…..እናቴ እንዴት እንደምትደነግጥ እና እንዴት እንደምትበሳጭብኝ ስገምት ትንፋሽ አጠረኝ..ግን የሆነው ካሰብኩት በተቃራኒው ነው … አናቴ ከተቀመጠችበት አልጋ ተስፈንጥራ በመነሳት ወለሉ መሀከል ተገትራ በመሳቀቅ ስታወራ የነበረችው ትርሲት ላይ ስትጠመጠምባት አይኔን አጨንቁሬ ተመለከትኩ..ጨምቃ ስታቅፋት…አገላብጣ ስትስማት
‹‹እንዴ እቴቴ ምንድነው……?የነገርኩሽን ሰምተሸል?››
‹‹አዎ ሰምቼያለው..ይሄ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ታውቂያለሽ..ልጄ ተአምራዊ በሆነ መልኩ ቀስ በቀስ የመዳን ተስፋው እየለመለመ መሆኑን ነው››
‹‹እንዴት… ?ይሄ ደግሞ ከመዳን ጋር ምን አገናኘው››እኔም በውስጤ ሥጠይቅ የነበረውን ጥያቄ ነው ትርሲት እናቴን የጠየቀችልኝ ..ከስንት ዓመት አሰልቺ ጥበቃ ቡሃላ ግራ እጁን ማንቀሳቀስ እና በመጠኑም ቢሆን መጠቀም ጀመረ…አሁን ደግሞ ውጫዊው የመራቢያ አካሉ ለውስጣዊው ስሜቱ መልስ መስጠት ጀመረ…የምለውን በቀላሉ ልትረጂኝ አትቺይም..ግን ይሄ ትልቅ የምስራች ነው…ብዙ የህክምና ፕሮፌሰሮች ማድረግ ያልቻሉትን ነው አንቺ በየዋህነት እና በንጽህ ፍቅርሽ ማድረግ የቻልሽው…እንዴት ይሄንን የመሰለ ዜና እስከዛሬ ትደብቂኛለሽ?››
‹‹እንዴ እቴቴ …ምን ብዬ እንደምነግርሽ እኮ ጨንቆኝ ነው….እኔ ጥፋት የሰራው መስሎኝ ፀፀት ላይ ነበርኩ››
‹‹የምን ጥፋት ..የምን ፀፀት››
‹‹አይ እቴቴ የዛን ቀን ሳጥበው ልብሴ እንዳይበሰብስ ስለፈለኩ በዛውም እኔም ገላዬን ልታጠብ ፈልጌ ስለነበር እራቁቴን ሆኜ ነበር …የነበረው..ማለቴ በፓንት ብቻ….እርግጥ የዛን ጊዜ አይደለም ያልኩሽ ነገር የተከሰተው…ሰውነቱን በማሸው ጊዜ ነው….. ››
ደግማ ስባ ወደ ደረቷ አስጠግታ ..በማቀፍ ግንባሯን ሳመቻት‹‹..ምን አይነት ውለታ እንደዋልሺልኝ አታውቂም..እንኳንም እንደዛ አደረግሽ..ምን አልባት የልጄ ድህነት ቁልፍ በዚህ መንገድ የሚገኝ ሊሆን ይችላል….፡፡
‹‹ማለት?››
‹‹አይ ተይው …እንዲሁ ነው..በይ አሁን ሂጂ ደህና እደሪ››
‹‹እሺ እቴቴ..አንቺም ደህና እደሪ››
‹‹እሺ ደህና እደሪ...ግን ከመሄድሽ በፊት ነገ ሰውነቱን ታጥቢልኛለሽ አይደል?››
‹‹እጠቢው ካልሽ እሺ..ደስ ይለኛል››
‹‹አዎ በደንብ እጠቢው…..እና ደግሞ ስታጥቢው ልብስሽ እንዳይረጥብብሽ አውልቂው…››
‹‹እንደዛ ይሻላል…››በፈገግታ እና በእፍረት
‹‹አዎ አንቺም እየታጠብሽ ብታጥቢው በጣም ደስ ይለዋል….››
‹‹እሺ እቴቴ››
‹‹..እና ደግሞ ሰውነቱ ዘና እንዲልለት ማሸቱንም እንዳትዘነጊ››
‹‹አልዘነጋም እቴቴ…››ብላ መኝታ ቤታችንን ለመጨረሻ ጊዜ ለቃ ወጣች፡፡አሁንም ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ውስጥ ያለው አስመስዬ አይኖቼን ጨፍኜ ግን ደግሜ በስሱ አጨንቁሬ መከታተሌን ቀጥያለው…. እናቴ የመኝታ ቤቱን በራፍ ከውስጥ ቀረቀረችና ግድግዳው ላይ በተሰቀለው የመድሀኒአለም ስዕል ፊት ለፊት ወለሉ ላይ ተንበረከከች..ዓይኖቾን ስዕሉ ላይ የእጆቾን መዳፎችን ደግሞ አንድ ላይ አጣምራ ወደ ግንባሯ አካባቢ አንከርፍፋ ፀሎቷን ማነብነብ ጀመረች
‹‹…..አምላክ ምንም እንኳን ዝምታህ ለእኛ ለደካሞቹ የዘላለም መስሎን ተስፋ ቢያስቆርጠንም አንተ ግን በትክክለኛው ቀን ትክክለኛውን መልስ መመለሱን ታውቅበታለህ…ይሄንን የመሰለ ተዓምራዊ ዜና ስላሰማሀኝ አመሰግናለው..ጌታ ሆይ ደግሞ አምናለው ልጄ በቅርቡ በሁለት እግሮቹ ይቆማል…ልጄ በእጆቹ ይመገባል…ልጄ አፍቅሮ የሴት ልጅ ከንፈር ይስማል… ከቆንጆ ጉብል ጋር ፍቅር ይጋራል…..አምናለው ልጄ የህይወትን ተአምራዊ በረከት የሚዘንብለት ሰው ይሆናል…ጌታ ሆይ ክብር ላንተ ይሆን ››በማለት ፀሎቷን አጠናቃ ወደ እኔ ስትመጣ አይኖቼ ፈጠው አንባዬ በግራ ጉንጬ ላይ ወደ ታች ሲንጠባጠቡ ነበር ያገኘቺኝ
‹‹ወይ!!! የእኔ ፀጋ… ነቅተሀል እንዴ ?ለምን ታለቅሳለህ….የሀዘን ዘመናችን እኮ እያከተመለት ነው..››በማለት አንሶላውን ገልጣ ከውስጥ ገባችና እቅፍ አድርጋኝ በእጆቾ እንባዬን እያበሰችልኝ…ፀጉሬን እያሻሸችልኝ…የእውነት በደስታ በተሞላ ሰላማዊ እንቅልፍ እንድዋጥ አደረገችኝ፡፡የማንነቴ ፈጣሪ ሀርሜ ኮ…..

💫ይቀጥላል💫

Like👍 ማድረግ እንዳይረሳ

አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን
👍81
#ሀርሜ_ኮ
:
ክፍል-ስድስት

:
:
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

...ሶደሬ ደርሰናል …….ከአዲስ አበባ ሶደሬ ድረስ ያሳለፍነውን የጉዞ ታሪክ ልተርክላችሁ አልፈልግም ..ምክንያም ብዙም የተለየ ትዕይንት የለውም….እንደደረስን ሶስት የተለያየ ማረፊያ አልጋ ተከራየን…በአንዱ ክፍል ትርሲት ልብሶን አስቀመጠችበት …. በሌላው ክፍል የሶስታችን ዕቃዎች ተቀመጡበት..ሹፌሩ ከእኛ እራቅ ያለ ሌላ ክፍል ተያዘለት….፡፡
የተወሰነ እረፍት አድረግንና ተሰባስበን ወጣን… ዘና ለማለት …፡፡እራታችን በልተን ሁሉን ነገር ጨርሰን ከምሽቱ 3 ሰዓት አካባቢ ወደ ማረፊያችን ተመለስን…ዊልቸሬን እየገፋች ያለችው ትርሲት ነች…..ልክ ጎን ለጎን የሚገኘው መኝታ ክፍላችን በራፍ ጋር ስንደርስ
..እኔን ለማስረከብ ዊልቸሬን ወደ እናቴ እየገፋች‹‹መኝታው አይበቃችሁም ማክዳ ከእኔ ጋር ትተኛ››አለች ትርሲት
‹‹አይ ይበቃናል››እናቴ ፍርጥም ብላ መለሰችላት
‹‹አረ እቴቴ… እኔም ብቻዬን መተኛት እፈራለው..?››
‹‹ለሊት ታስቸግርሻለች..ባይሆን ፀግሽ ካንቺ ጋር ይተኛ››
‹‹ምን..?››አለች በድንጋጤ ወደ እናቴ ስትገፋ የነበረውን እኔ የተቀመጥኩበትን ዊልቸር መልሳ ወደ ራሷ እየሳበች
‹‹እንዴ ምን አስደነገጠሸ....?ብቻዬን መተኛት እፈራለው የምትይ ከሆነ ፀግሽን ወሰጂው››
አይደለም እሷ እኔም በጣም ነው የደነገጥኩትም የተደነጋገርኩትም…..እናቴ ምን ማለቷ ነው....?እንዴት ከእኔ ይልቅ ማክዳ አብራት እንድትተኛ ፈለገች…...?ውስጤ የተፈጠረ ጥያቄ ነበር…ቅር ያለኝ መሰለኝ ..ግን ደግሞ ከቅሬታዬ ባሻገር ጎላ ያለ የደስታ ስሜት እየተሰማኝ ነው…ከትርሲት ጋር ለመተኛት አጋጣሚውን በማግኘቴ የመጣ ደስታ
‹‹እ ምን ወሰንሽ..?››
‹‹አረ እሺ›› ብላ ስትገፋው የነበረውን ዊልቸሬን ጠምዝዛ እየገፋች የእሷ ዕቃዎች ወደ አሉበት ወደ አንደኛው ክፍል ይዛኝ ከገባች ቡኃላ…‹‹ደኅና እደሩ››አለቻት
‹ደህና እደሩ..ፀግሽ ደህና እደር››እናቴ ነች
ትርሲት በራፍን ዘጋችው‹‹….ወይኔ አላመንኩም…በቃ እኮ ባልና ሚስት መሆናችን ነው››አለችኝ ሳቅ በሳቅ ሆና..ዊልቸሬን ወደ አልጋው አስጠጋችና ጎንበስ ብላ ጫማዬን ከእግሬ ላይ አወለቀችልኝ… ቀስ ብላ ወደ አልጋው ገለበጠችኝ… ቀና ልትል ስትል በዛችው ብርቅ የሆነችውን ግራ እጄን አንቀሳቀስኩና የለበሰችውን የቲሸርት እጅጌ ጨምድጄ በመያዝ ወደ ራሴ ስቤ አስቀረዋት
‹‹….እንዴ!!! አንተ ጉዳኛ..ምን ፈለክ..?››መጎተቴን ቀጠልኩ
‹‹እሺ እሺ….መሳም አምሮህ ነው አይደል..? ብላ ከንፈሬ ላይ ተጣበቀችብኝ…. የፈለኩት ነገር ስለነበረ ዘና ብዬ እመጠምጣት ጀመር…መሳሞን ሳታቋርጥ ቀስ ብላ በአንድ እጇ ተራ በተራ ጫማዋን አወለቀች…እናም ወደ አልጋ ሙሉ በሙሉ ወጣች..ቀኝ እጆን አንገቴ ስር አሾልካ አስገባችና ግራ እጆን ጭንቅላቴ ላይ አድርጋ ፀጉሬን እያሻሸችልኝ ልዩ ገነታዊ ወደሆነ አለም ውስጥ ከተተችኝ..ምን እንደሚሰማኝ ሙሉ በሙሉ ለመናገር ሁሉ አልችልም…እንደምንም ከንፈሯን ከከንፈሬ አላቃ ግንባሬን እየሳመች ..ጉንጬን እየሳመችኝ …አንገቴን እየሳመቺኝ….‹‹ታፈቅረኛለህ አይደል..?››ስትል ጠየቀችኝ
ግራ እጄን ወደ ቀኝ ጡቷ ልኬ ጠንከረ አድርጌ ጨመኳት‹‹አዎ በጣም..እጅግ በጣም አፈቅርሻለው››ማለቴ ነው…እስቲ በእግዚያብሄር ጡት መጭመቅ እና አፈቅርሻለው የሚለው ቃል በምንኛ ነው የሚገናኘው..?
እሷ ግን የልብ አውቃ ነች..ወዲያው ነው የተረደችኝ‹‹ያን ያህል ነው ምታፈቅረኝ..?››
ግራ እጄን ወደ ግራ ጡቶ አዘዋወርኩና ይበልጥ ጠንከር ባለ ኃይል ጨመቅኳት‹‹ወይኔ ታድዬ ብላ ወደ ከንፈሬ ተመለሰችና ስትመጠኝ … ያለንበት ክፍል በራፋ ተንኳኳ…
ደንግጣ በተለየ ቅልጥፍና ከተኛችበት ተነሳችና ከአላጋው በመውረድ ‹‹ማነው..? ››አስትል ጠየቀች
‹‹እኔ ነኝ…ተኛችሁ እንዴ..?››የሀርሜ ድምፅ ነበር
‹‹እንዴ እቴቴ…አንቺ ነሽ....?አልተኛንም››ይሄንን የምታወራው… ቀሚሶን ወደ ታች እየጎተተች..የተዛነፈው ቲሸርቷን እያስተካከለች ነው….፡፡ቁልቁል እኔን እያች ..በማፈር እና በድንጋጤ መካከል ሆና በራፍን ልትከፍትላት እርምጃ ከጀመረች ብኃላ መልሳ ወደ እኔ በመምጣት አልጋ ልብሱን ከባዶ የአልጋው ክፍል ሰብስባ ከወገቤ በተች ያለውን ሰውነቴን አለበሰችኝና….‹‹ይሄንን ብልግናህን እናትህ ማየት የለባትም›› ብላ ዝቅ ባለ ድምጽ ወደ ጆሮዬ ተጠግታ ነገራኝ ወደ በራፉ ሄደች…ለምን አልጋ ልብሱን እንዳለበሰቺኝ ገባኝ…የተቀሰረ ብልቴን እናቴ እንዳታይ መከለሏ ነው….የደስታ ፈገግታ ፈገግ አልኩ…..
‹‹ግን እናቴ ምን ነካት....?ከእንዲህ አይነት ታሪካዊና ወሲባዊ ቁርኝታችን እንዴት ታናጥበናለች....?ምን ፈልጋ ነው የምታንኳኳው...?እንዴ ምን ነካኝ …..?እኔ እኮ እድሜ ዘመኔን ሙሉ የእናቴን ኮቴ እንደሞዛር ሙዚቃ ሳጣጥም የኖርኩ ሰው ነኝ..እኔ እኮ የእናቴን ወደእኔ አካባቢ የመቅረብ ሽታ ልክ እንደናርዶስ ሽቶ ወደ ውስጤ ..ነፌሴ ድረስ ዘልቆ እንዲሰማኝ በመሳብ ስረካና ስደሰት የኖርኩ ሰው ነኝ….እኔ እኮ እድሜ ልኬን የእናቴን ወደ እኔ ክፍል የመምጣት የሚያበስረውን ድምጾን ስሰማ ለእምዬ ማርያም ከመላአኩ ገብርኤል መንፈሳዊ አንደበት የወጣ የብስራት ድምጽ በደረሳት ጊዜ እንደተሰማት አይነት ደስታ ሲሰማኝ የኖርኩ ሰው ነኝ..እና ለምንድነው ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ የእናቴን ድምጽ መስማቴ በውስጤ ቅሬታ የፈጠረብኝ…...?እንዴት የእናቴ ወደ እኔ ክፍል ለመግባት መፈለጓ ደስ ሳያሰኘኝ ቀረ…..?
ብቻ በራፉን ከፈተችላትና እናቴ ወደ ውስጥ ገባች….
‹‹ምነው እቴቴ ሰላም ነው..?››
‹‹አይ ሰላም ነው..ግነ ሀሳቤን ቀይሬ ነው››ይሄንን የምትናገረው በራፉን አልፋ ወደ ውስጥ ዘልቃ ፊት ለፊት ቆማ ሁለታችንንም እያፈራረቀች እያየችን ነው..ደግሞ በሁለት እጆቾ ሁለት የተለያዩ በፔስታል የተጠቀለለ ዕቃ ይዛለች
‹‹ምን ይሆን..?››
‹‹የትኛውን ሀሳብ….?››
‹‹ይገርምሻል… ማክዳ አልተኛም ብላ የምታስቸግር መስሎኝ ነበር..አሁን ስለደከማት መሰለኝ ገና ጎኗ አልጋው ላይ ከማረፉ ነው ጭልጥ ያለ እንቅልፍ የወሰዳት…››
እናቴ ምን እያለች እንደሆነ አልገባኝም…
‹‹አሪፍ ነው ››ትርሲት መለሰች ግራ መጋባቷን በሚሳብቅ ድምፅ ቅላፄ
‹‹ስለዚህ አታስቸግርሽም ማለት ነው...››
‹‹ማ..? ማክዳ እኔን..?››
‹‹አዎ ሰለተኛች አታስቸግሪሽም… ስለዚህ ሂጂና ከእሷ ጋር ተኚ››
‹‹ከእሷ ጋር…ለምን .?አንቺስ..?››ጥያቄዋን አግተለተለች
‹‹እንዴ እኔማ እዚህ ተኛለው..ከልጄ ጋር››ኮስተር ብላ መለሰች
ፈክቶ የነበረው ፊቴ ሲጨልም ለእኔ ለራሱ ይታወቀኛል….በፍትወት ስሜት ግሎ የነበረው ሰውነቴ አሁን በንዴት ኩምሽሽ ማለት ጀመረ…እንዴ ሀርሜ ምን ነካት…..?ለእሷስ ቢሆን እድሜ ልኳን ከእኔ ጋ መተኛት አይሰለቻትም…...?ቅድም ሀይቁ ዳር ቁጭ ብለን በተመስጦ ና በፅሞና ስንዝናና ያየውት በቅርብ እርቀት የነበረ አንድ ሽበታምና ደንደን ያለ ሙሉ ሰው ትዝ አለኝ….ለምን ትዝ አለኝ መሰላችሁ.? …እናቴ ላይ አፍጧባት ነበር….አይኖቹን ከእሷ ላይ መንቀል አልቻለም ነበር…ደግሞ እራት ስንበላም በአቅራቢያችን ሲያንዣብብ አይቼዋለው..እሷም አንድ ሁለቴ በመገላመጥ ስታየው እና በመገረም ስትሸረድደው ታዝቤለው…እና ምን አለ አሁን ማክዳ ከተኛችላት ወጣ ብትል….?እርግጠኛ ነኝ አሁን ካለንበት ክፍል በአስር ሜትር እርቀት አይጠፋም…እና ከእሱ ጋር ዘና ለማለት ብትሞክር መቼስ እናቴን ገና ጮርቃ ልጅአገረድ ነች ባልላችሁም በእሷ ዕድሜ አካባቢ ያለን ማንኛውንም ወንድ ማማለል
👍10
የሚያስችል ቁመና፣ መልክና ተክለሰውነት ያላት ግሩም ሙሉ ሴት እንደሆነች በድፍረት መመስከር እችላለው..እርግጠኛ ነኝ እኔ ከጎኖ ባልኖር ኖሮ እስከዛሬ ብቻዋን ያለባል የምትኖር አይነት ሴት አልነበረችም…እና ቢያንስ ዘና ለማለት አሁን ሰውዬው ጋር ወጣ ብትል ብዬ አሰብኩ…ግን አንዴት እንደዛ ላስብ ቻልኩ…..?.እንዴት የእናቴ ብቸኝነት እሰከዛሬ ሳያሳስበኝ ዛሬ ሊያሳስበኝ ቻለ…...?ሁለት ምክንያት ነው ያለኝ፡፡አንደኛው እናቴ ዘና ለማለት ወጣ ብትል…እኔም እዚህ ከትርሲት ጋር የጀመርኩትን ፍቅር እቀጥላለው በሚል እሳቤ….ሁለተኛው ግን እናቴ ለዘመናት ምን እንዳጣች በደንብ ያወቅኩት ሰሞኑን በተለይም ዛሬ ስለሆነ ነው..ከሚወዱት ሰው ከንፈር ላይ ከንፈርን ማጣበቅ ምን አይነት ደስታ እንደሚያጎናጽፍ አሁን ነው የተረዳውት…በሚያፈቅሩት ሰው መታቀፍ..በሚወዱት ሰው መዳሰስ….እነዚህ ነገሮች አንድ በህይወት ላለ ጤነኛ ሰው ለመኖር ከሚያስፈልገው አየር እኩል ዋጋ ያላቸው መሰረታዊ የደስታው መፍለቂያ ሪሞቶች መሆናቸውን መረዳቴ ነው….እናቴ ይሄንን ነው የሰዋችው..ለእኔ ለልጇ ስትል..፡፡ለአንድ ቀን አይደለም..ለግማሽ ዕድሜዋ..፡፡እኔ ግን ለሽርፍራፊ ሰከንድ ከነበርኩበት የደስታ መንደር ስላወጣችኝ ቅሬታ ተሰማኝ..አይገርምም..? …
‹‹እቴቴ…አረ እዚህ ብተኛ ይሻለኛል››
‹‹እንዴት ይሻለኛል..?››
‹‹ማለቴ....?ምን መሰለሽ..?›…››ምትናገረው ጠፋባትና በንዴት ጉንጮቾ ቀሉ..እናቴ ፈገግ አለች
ትርሲት‹‹በቃ እሺ እንዳልሽ…››ብላ ወደ እዛኛው ክፍል መራመድ ጀመረች
‹‹አረ ቀስ በይ….ስቀልድ ነው…ቅድም ገዝቼልሽ ሳልሰጥሽ ስለረሳው ይሄንን ልሰጥሽ ነው የመጣውት….››ብላ በቀኝ እጇ ይዛው ነበረውን ፔስታል አቀበለቻት
‹‹ምንድነው..?››
‹‹ስጦታ ነው… ይሄ ደግሞ ያንተ ነው››ብላ በግራ እጆ የነበረውን ፔስታል አልጋው ላይ ከጎኔ ወርወር አድረገችው..
ትርሲት እናቴን‹‹አመሰግናለው..››ብላ ተንጠራርታ ጉንጮን ሳመቻት
እኔም ተጨማዶ የቆየውን ፊቴን በፈገግታ ተረከኩት ….እንዲህ ሰላሳ ሁለት ጥርሶቼ የተሰጡት እናቴ ለሰጠችን ስጦታ ሳይሆን ትረሲት ከእኔ ጋር የማደሯ ጉዳይ አሁንም ባለመሰረዙ ነው….አናቴ ጎንበስ ብላ ግንበሬን ሳመችኝና…. እሷንም ጉንጮን ስማ‹‹..በሉ ደህና እደሩልኝ….በጣም እወዳችሆለው…››ብላ ወደ በራፉ እርምጃ ጀመረች
‹‹እኛም እንወድሻለን››አለች ረትርሲት እኔንም ወክላ…እናቴ ሄደች ትሪሲት በራፍን ቀርቅራ እየፈነጠዘች መጣች….
‹‹ይህቺ እቴቴ ግን ተንኮለኛ ነች….ካንተ ልትለየኝ መስሎች ከፍቶኝ ነበር….›› አለቺኝ…እኔም ተመሳሳይ ስሜት ተሰምቶኝ እንደነበር በምልክት ነገርኳት
እስቲ ስጦታው ምን ይሆን.? ልየው ብላ ፔስታሉን ከፈተች እና እጇን ወደ ፔስታሉ ሰዳ አወጣችው …ስስ ሮዝ ከለር ያለው የሚያምር ስስ የለሊት ልብስና የሚያማምሩ ሶስት ፓንቶችን ናቸው…‹‹ወይኔ ሲያምሩ .?ቆይ ያንተስ ምንድ ነው.?››ብላ ወደ አልጋው ጎንበስ አለችና ለእኔ የመጣውን ስጦታ ከፔስታሉ አወጣችው…‹‹ሚያምር ጋዎን ፒጃማ እና ተመሳሳይ ቁጥር ያላቸው ፓንቶች ናቸው
‹‹አይ እቴቴ….አለች ትርሲት እየተፍለቀለቀች…ቆይ እንደውም ልለካው..››አለችና የለበሰችውን ቀሚስ አወለቀች…ብስል ቀይ ገላዋ ለእይታ ተጋለጠ …ቀይ ቀለም ያለው ጡት መያዣዋ ጡቶቾን በግልጽ እናዳላይ ከልለውኛል…ግን መቀሰራቸውን ማየት ብቻ ልብን ያርዳል እና ተመሳሳይ ቀይ ቀለም ያለው ፓንቷ ይታየኛል፡፡
ከፓንቶቹ መካከል አንዱን አነሳች…‹‹እንዴ ምን ነካኝ .?እንዴት አድርጌ ልለካው›››ግራ በመጋባት አፍጥጣ እያየችኝ ጠየቀችን
‹‹አንተን እኮ ነው..ፊትህን ወደ እዛ አዙርልኝ ..››
ይበልጥ አይኖቼን በልጥጬ አፈጠጥኩባት
‹‹‹ምን አይነት ፈጣጣነው በእግዚያብሄር…‹‹ብላ ፊቷን ከእኔ በተቃራኒው አዞረችና የለበሰችውን ፓንት ወደ ታች ሳበችው..ጎንበስ ብላ ከእግሮቾ አሾልካ ለማውለቅ ጎንበስ ስትል ችምችም ባለ ቁጥቋጦ ደን የተሸፈነውን ስንጥቅ ስምጥ ሸለቆዋን በከፊል ሾፍኩት…….በእሷ ቤት ስለዞረች አይታይም አሉ…. ከዛ አዲሱን ፓንት አደረገችና ‹‹..አያምርም…እየው እስቲ ..››ልክ በተለያ የፈረንጅ ቻናሎች እንደማያቸው ሞዴሎቹ እየተምነቀነቀች እና እየተውረገረገች በመሽከርከር አስጎበኘችኝ ..ከዛ ቢጃማዋን አነሳችና ለበሰችው…ስስ ከመሆኑ የተነሳ መላ ሰውነቷን ወለል አድርጎ ያሳያል..ቢሆንም ግን ያምራል…ያምራል ብቻ ሳይሆን ያማልላል..ያማለለኝ ግን ቢጃማው አይመስለኝም በቢጃማው የተጠቀለለው ውቡ ገላ እንጂ…
በል እንግዲህ የእኔን ስጦታ በደንብ ጎብኝተሀል አሁን ተራው ያንተ ነው በማለት ቅድም አልብሰኝ የነበረውን አልጋ ልብስ ከሰውነቴ ላይ ገፈፈች..ከዛ የሱሪዬን ቁልፍ ፈታች..ከዛ ዚፑን ወደ ታች አንሸራተተችው….ከዛ ሱሪያን እየጎተተች ከእግሮቼ ላይ ሞሽልቃ አወለቀችውና ኮመዲኖ ላይ ወረወረችው….ከዛ ከውስጥ የለበስኩትን ሰፋ ያለ ፓንት በተመሳሳይ ሁኔታ አወለቀችውና ሱሪውን ያስቀመጠችበት ቦታ አስቀመጠች…፡፡ከወገቤ በታች እርቃኔን ቀረው.‹‹.ቆይ ቆይ ከላይ ያለውም መውለቅ አለበት›› አለችና የለበስኩትን ቲሸርት ከነ ውስጥ ካኔቴራው ወደ ላይ ጠቅልላ አወለቀችው…ሙሉ በሙሉ እርቃኔን ቀረው..‹‹አሁን ያንተን ፓንት እንሞክረው ከዛ ጋዎንህን ታደርግና ተቃቅፈን ለጥ ነው..››ብላ ወደ ፓንቱ ልትዞር ስትል እጆን ቀጨም አድርጌ ያዝኮት…
‹‹እንዴ ምነው.?››
ጎተትኮት
‹‹ቆይ መጀመሪያ ላልብሰህ››አልሰማዋትም…በአንድ እጄም ቢሆን መጎተቴን ገፋውበት … እርቃን ገላዬ ላይ ስቤ አጣበቅኮት..‹‹አንተ ልጅ ይሄ እጅህ በጣም እየጠነከረ እና እያንገላታኝ ነው››ብላ ወቀሳ በሚመስል ግን በደስታ በተወጠ ሰሜት እንድትለጠፍልኝ ከፈለግኩት በላይ ተለጠፈችብኝ…እንድታቅፈኝ ከፈለኩት በላይ ጨመቀቺኝ…እንድትስመኝ ከፈለኩት በላይ መጠጠቺኝ..ይህቺ ልጅ መቼስ እግዜር ነው ላሳለፍኩት የሠለፈ ደባሪ ህይወቴ ማካካሻ የሸለመኝ… እንጂማ አሁን እኔ ለፍቅር የምመረጥ ሰው ነኝ..አሁን እኔ በፍቅር የምሳም በፍቅር የምላስ ሰው ነኝ…እንዲሁ ፈርዶባት እንጂ …፡፡ስታሳዝን

💫ይቀጥላል💫

Like👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን
👍41
#ሀርሜ_ኮ
:
ክፍል-ሰባት
:
:
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

...በውበት እና በፍቅር ያሸበረቁ ሁለት የእረፍት ቀናቶችን በሶደሬ አሳልፈን ወደ ቤት ከተመለስን ሶስት ቀናቶችን ሆኗናል፡፡ከረፍት እንደተመለስን እናቴ አንዳንድ ስር ነቀል የሆኑ ለውጦችን በቤት ውስጥ አካሄዳለች..በመጀመሪያ ያደረገችው ለቤቱ ሌላ ሰራተኛ መቅጠር ነው ይሄን ስትሰሙ መቼስ ሳትደነግጡ አትቀሩም ትርሲትስ ምን ልትሆን ነው…?ከእናትህ ተጣላች እንዴ…?ወይስ በቃኝ ወደ አሜሪካ ልብረር አለች..?ይሄ በውስጣቹሁ ሚመጣ ወይም የሚፈጠር ጥያቄ ነው..ግን ሌላ ሰራተኛ ያስፈለገው ትርሲትን ሙሉ በሙሉ ከስራ ጫና ለማላቀቅ ነው..ይሄ የሀርሜ ውሳኔ ነው..በቃ ያንቺ ዋና ስራ ፀግሽን መንከባከብ ብቻ ነው ተብላለች፡፡
ሌላው የተወሰደው ስር ነቀል ለውጥ እኔ መኝታ እድሜ ልኬን ከተዳበልኳት ከእናቴ መኝታ በመነጠል ወደ ትርሲት መኝታ ቤት ተዘዋወርኩ…ይሄም ቀጥታ በእናቴ ትዕዛዝ የሆነ ነው….
ሌላው ሁል ግዜ አንቴ ከስራዋ እንደመጣች ትርሲትን ከእኔ ነጥላ ወደ ክፍሎ ትወስዳትና ለአንድ ሰዓት ያህል ታወራታለች…ምን እንደምታወራት በጣም ለማወቅ ብጣጣርም እየደጋገምኩ ብጠይቃትም ትርሲትም ፍንክች ልትልልኝ አልቻለችም…ግን በእናቴ ተመክራ ከመጣች ብኃላ በየቀኑ አንድ የተለየ እና ዓዲስ ነገር በእኔ ላይ ታደርጋለች….ሰውነቴን ማሸት….እግሮቼን ማንቀሳቀስ…የእጆቼን ጣቶች ማነቃነቅ …ደግፋኝ መቆም ..በእየእለቱ የምታደርገው ነገር ነው ፡፡
ይሄንን ነገር ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ፕሮፌሽናል በሆኑ ቴራፒስቶች ጋር ሞክሬው ተስፋ የለሌውና አበሳጭ ሁኔታ ብቻ ሆኖብኝ የተውኩት ነገር ነው..አሁን ግን በአማተሯ ፍቅረኛዬ ባልጠና ሁኔታ እየተከወነ ቢሆንም ግን ደስ እያለኝ ነው የማደርገው…እያንዳንዶን የሰውነቴን ክፍል ስትነካኝና ስታነቃንቀው የሆነ የዘመናት ድንዛዜዬ ከውስጤ ቀስ በቀስ ሲተን ይታወቀኛል… እየታየኝ ነው እና አርግ ያለችኝን ሁሉ ማድረግ ቢያቀቅተኝ እንኳን ቢያንስ በሀሳቤ እሞክራለው..እርግጥ ለማድረግ የምትጥረው ጥረት በሙሉ የእሷ ሀሳብ እንዳልሆነ ከገባኝ ከራርሞል ..ከጀርባው የሀርሜ ምክር አለበት…የእሷ ስልጠና አለበት…የእሷ ጉጉት አለበት….ሀርሜ ይህቺን ትርሲት ለእኔ ዕፀ ድህነቴ እንደምትሆን ተስፋ ማድረግ እና ማመን ከጀመረች ሰነባብታለች..ይሄንን ደግሞ ከንግግሯ ከሁኔታዋ እና ከአይኖቾ ውስጥ በየቀኑ አነበዋለው…..እኔ ግን ባለው ነገር ደስተኛ ነኝ…አሁን በውስጤ በሚሰማኝ ነገር ደስተኛ ነኝ..በውስጤ በሚዘንበው የፍቅር ዝናብ መላ ውስጠቴ ደስታ እየረሰረሰ ነው…ለምን ተፈጠርኩ ብዬ ለዓመታት ፈጣሪን ስጠይቅና ስወቅስ የኖርኩት ልጅ አሁን እንኳንም ፈጠርከኝ ለማለት በቅቼያለው…ትርሲትን ከምነግራችሁ በላይ አፍቅሬያታለው…ለደቂቃም ከፊቴ ዞር ስትል በድቅድቅ ጨለማ መብራቱ እንደጠፋበት ቤት ውስጤ ጭልም ይልብኛል..ወደ ውጭ የሆነ እቃ ልግዛ ብላ ስትወጣ ተመልሳ የምትመጣ አይመስለኝም….ከእኔ የተሸለ ሎጋ ወጣት ቢለክፋትስ…?ከእኔ የተሸለ ዘናጪ ቢጠልፋትስ…?
የምትፈልገውን የሚሰጣት..የሚያምራትን ቀሚስ የሚገዛላት…ትልቅ ሆቴል ወስዶ የሚጋብዛት ብታገኝስ..?ልግባሽ የሚላት ባለቤትና መኪና ቢያማልላት እና ቢወደስድብኝስ.?በውስጤ እየተንፈራገጠ የሚያሰቃኝ ስጋት ነው….ይሄንን ሳስብ በተአምርም ቢሆን መዳን እንዳለብኝ ይሰማኛል…ጤነኛ ሆኜ በእግሮቼ መራመድ እንዳለብኝ …እጆቼን አንቀሳቅሼ መስራትና መብላት..በእሷ እጅ መጎረስ ብቻ ሳይሆን እሷንም ማጉረስ እንዳለብኝ ወስናለው…አንደበቴ ተላቀው ቃላት ማውጣት ..ከውስጤ ስለእሷ ምን እንደሚሰማኝ ..ምን ያህል እንደማፈቅራት..ላገባትም እንደምገፈልግ በጆሮዋ ልነግራት እፈልጋለው..አዎ መዳን አለብኝ..ዉሳኔዬ ነው..ግን እንዴት ነው በሀያ ሶስት አመት ሙካራ ያልተሳካልኝን የመዳን ጥረት በሳምንታት ውስጥ ተስፋ ማድረግ የቻልኩት፡፡
አሁን ያለውት ሳሎን ውስጥ ነው ፡፡ማታ ነው ከምሽቱ ሶስት ሰዓት አካባቢ..ቀስ በቀስ የቤቱ ሰዎች ሁሉ መጥተው ሳሎኑን አድምቀውታል…ውጭ የቀረው የቤቱ አባል መሀሪ ብቻ ነው..የእኔዋ ትርሲት ፊት ለፊት አጠር ያለች ኩርሲ ላይ ተቀምጣ ትታየኛለች..ከፊት ለፊቷ በመለስተኛ ረከቦት ላይ እንደ ሰለጠነ ሰራዊት በተርታ የተሰለፉ አስር የሚሆኑ ነጫጭ ሲኒዎች ከረከቦቱ ጎን ጥቁር ጀበና ከፊት ለፊቱ የእጣን ጢስ የሚትጎለጎልበት ጊርጊረ ይታያል…አያችሁ ይህቺ ልጅ ምን ያህል ቀልቤን እንደተቆጣጠረችው..አሁን እንኳን ስለቤታችን ሁኔታ ስገልጽላችሁ ከሷው ነው የጀመርኩት..
ለማኝኛውም ቀጠልኩ…እናቴ ከእኔ ያለውበት ሶፋ ላይ ነው የተቀመጠቸው ጭኗ ላይ ጭንቅላቴን አንተርሳ ፀጉሬን እየዳበሰችልኝ….ከእኛ በቅርብ እርቀት እናትና ልጅ ተቃቅፈው ይታዩኛል ፌናን እና ማክዳ …ከነሱ ፈንጠር ብላ ሮሚ አቀርቅራ ካልኩሌተረ እየጠቀጠቀች ማስታወሻ ደብተሯ ላይ ትሞነጫጭራለች…አዲሷ ሰራተኛ ፊት ለፊት የለችም… ማአድ ቤት ስራ እየሰራች ሳይሆን አይቀርም
‹‹ፌን መች ነው ምርቃታችሁ››እናቴ ነች ጠያቂዋ
‹‹ሀያ ቀን ቀርቶታል››
ልትገላገይ ነዋ››አለቻት ሮሚ የምትሰራውን የሂሳብ ስራ አቋርጣ
-ምን መገላገል አለው…ስኮላር ሺፕ እሞከርኩ ነው..ከተሳካልኝ ወደ ውጭ ሄጄ ትምህርቴን ቀጥላለው››
-ቀጥላለው..››በመደነቅና በመንገሽገሽ ጠየቀቻት
‹‹ምነው አዎ ቀጥላለው››
-ትቀልጂያለሽ እንዴ..ሰባት አመት እኮ ነው የተማርሺው..አሁንም ቀጥላለው ስትዪ ትንሽ አይደብርሽም››
-ለምን ይደብራታል››እናቴ ጣልቃ ገባች
እንዴ እሺ ትምርቱ አይሰልቻት..ደሞዝ መብላት አያምራትም››
-ያምረኛል..ግን ገንዘብ ከመልመዴ በፊት ትምህርቴን ያሰብኩት ቦታ ማድረስ አለብኝ››
-አረ አትጃጃይ. ያንቺ ትምህረት መድረሻው አይታወቅምና…እድመሜሽን ወረቀት በማገላበጥ ትጨርሺዋለሽ..›
አየሽ ለአንቺ ሰባት አመት መማር የሰማይ ያህል ከባድ መስሎ ሊሰማሽ ይችላል..ግን ስለሰው ልጅ ጤና ነው የምንማረው..ህይወትን ስለማዳን ነው የምንማረው..ለዛ ደግሞ በቂ አይደለም.አሁን አጠቃላይ ሀኪም ሆኜ ነው የተመረቅኩት ግን ስፔሻላይዝድ ማድረግ እፈልጋለው..
ጎሽ ልጄ ..እሷን አትስሚያት…ለመሆኑ ከቀናሽ በምንድነው ስፔሻላይዝድ ማድረግ የምትፈልጎው››
በትክክል በዚህ ብዬ አልወሰንኩም ፡፡ግን አንድ ነገር እርግጠኛ ነኝ..በቀጣይነት ምማረው የህክምና ትምህርት ውንድሜ ጤና ላይ ቅንጣትም ቢሆን ለውጥ እንዳመጣ የሚያግዘኝ መሆን አለበት..ቀኝ እጁን ማንቀሳቀስ እንዲችል ብረዳው…ወይንም የእግሮቹን ጣቶች እንዲታዘዙለት ማድረግ ብችል..ከላሆነ አንደበቱ ተላቀው ቃላት እንዲያወጣ ልረዳው ብችል..አዎ እድሉን ባገኝ ይንን ብቃት የሚሰጠኝን ትምህርት ነው የምማረው..ለዛ ደግሞ አልሰለችም…ከአሁን ቡኃላ 19 ዓመት እንኳን ቢወስደብኝ አይሰለቸኝም… እማራለው…ያንን ማደረግ ስችል ነው የእውነት እንደተማርኩ የሚሰማኝ……
ይሄንን ስትናገር እናቴ እንባዋ መንጠባጠብ ጀምራ ነበር..ትርሲትም እሷን ተከትላ መነፍረቅ ጀመረች.. ሮሚ እንኳን የጀመረችውን ክርክር ትታ በሀዘኔታ አፍጥጣ ስታያት ቆየችና ከተቀመጠችበት በመነሳት ልጆን አቅፋ ወዳለችው ፊናን በመሄድ አቅፋ ግንባሯን ሳመቻትና ‹‹የእኔ እህት በእውነት ሀሳብሽ ድንቅ ነው..በጣም ነው ስሜቴን የነካሽው..››ግን ለፀግሽ የአንቺ እንደዚህ ህይወትሽን ከባድ በሆነ ሁኔታ ከወረቀት ጋር መታገል የለብሽም››
‹ለምን የለብነኝም››በቁጣ ጠየቀቻት
‹አትቆጬ ..ለወንድሜ እኔ አለውለት ፣፣ሁለት አመት ብቻ ስጡኝ …ሁለት አመት ከዛ ቡሃላ ታይላንድ ሆነ ሆላንድ፤ ደብብ አፍሪካ ሆነ
👍15
አሜሪካ ብቻ ይድናል የተባለበት ቦታ ወስጄ አሳክመዋለው…ለምን መሰልሽ እንዲህ ከሰሜን ወደ ደብብ እየተስፈነጠርኩ ምባክነው ፡፡ሀብታም የመሆን ሱስ ኖሮብኝ…?አዎ አልዋሽም ሀብታም መሆን እፈልጋለው..ግን ሀብታም መሆን የምመኘው ለውድሜ ነው ::ወንድሜን በብሬ ማዳን ስለምችል…››
እቤቱ ሁሉ ለቅሶ በለቅሶ ሆነ..እኔም እንባዬን በውስጤ አግጄ ማስቀረት አልቻልኩም..
ይቅርታ እኔ ይሄንን እቺ ስለጀመርሺው እንጂ ቀኑ እስኪደርስ መናገር አልፈልግም ነበር.››እያለች የፈሰሰ እንባዋን እየጠረገች ሳሎኑን ለቃ ወደ ውስጥ ገባች
በዚህ ጊዜ የሳሎኑ በራፍ ተከፈተ…ቢኒያም መምጣቱ ነው…ወደ ውስጥ ዘለቀና እንደመንገዳገድ እያለ ወደ እኛ ቀረበ… ጎንበስ አለና የእናቴን ጉልበት ሳመ…
ከለበሰው ግብዳ ጥቁር ሌዘር ጅኬት ውስጥ ፕላስቲክ እሽግ የማንጎ ጅውስ አወጣና በግራ እጅ አስጨበጠኝና ግንባሬን ሳመኝ…ወደ ሌላው ኪሱ እጁን ሰደደና ቸኮሌት አውጥቶ እናቷ ጭን ላይ ለተቀመጠችው ለማክዳ ወረወረላትና ምንም ቃል ከአንደበቱ ሳይወጣ እየተንገዳገደ ወደ መኝታ ቤቱ አመራ ….እናቴ አዲሷን ሰራተኛ ጠራቻትና ከመተኛቱ በፊት እራቱን መኝታ ቤቱ ድረስ እንድትወስድለት አዘዘቻት…በለቅሶ የታጀበው የቡና ሴርሞኒ ተጠናቆ ራታችንን በልተን ሁላችንም ወደ መኝታችን ተበታተን…ያው እኔ እንደነገርኳችሁ ከትርሲት ጋር ወደ ምጋረው አዲሱ መኝታ ክፍሌ…››
ገብተን በራፉን ዘጋግታ አልጋ ላይ እንደወጣን‹‹
‹ቀናውብህ..በጣም ነው የቀናውብህ››አለቺኝ
አይኖቼን አንከባለልኮቸው‹‹ለምን ቀናሺብኝ ማለቴ ነው››
እንዴ እዚህ ቤት ያለው ሰው ሁሉ በጣም ነው እኮ የሚወዱህ..ሁሉም እኳ የገዛ የወደፊት ህይወታቸውን ሰውተው ላንተ ሲሉ ነው የሚለፍት…ይሄ ሰካራም ወንድምህ እንኳን እንዲህ አንደበቱ እስኪተሳሰር ድረስ ስክሮ ላንተ የሆነ ነገር ገዝቶ መምጣቱን አይዘነጋም…በእውነት ያበሳጫል››አለች
የተናገረችው ነገር ለምን እንደሚያበሳጭ አልገባኝምና..በግራ እጄ ጭኖ ውስጥ ገብቼ ልቆነጥጣት ሞከርኩ
-እረፍ እንጂ እወነቴን ነው ያበሳጫል..ምንም እንኳን እህቶችህ ቢሆንም ከእኔ በላይ እንዲህ ሲያስብልህ ሳይ እበሳጫለው..እኔ ብር የለኝ ወይም እወቀት የለኝ.ታዲያ ምኔን ተጠቅሜ ነው አንተን ለማዳን መጣር ያለብኝ….
-ዘንድሮ መዳኛዬ ደረሰ እንዴ…?ብር..እውቀት እና ፍቅር እኔን ለማዳን በየፊናቸው እየተሯሯጡ ነው ..የትኛው ይሳካለት ይሆን..አብረን እናየዋለም

💫ይቀጥላል💫

Like👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን
👍7
#ሀርሜ_ኮ
:
ክፍል- 8

:
:
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

...አሁንም ዙሪያዬ በብርሀን እንደታጠረ ነው ..ውስጤ በፍቅር እንደተጥለቀለቀ ነው፡፡ውስጤ ይራመዳል..ውስጤ ይሮጣል…ዉስጤ በትርሲት ልብ ውስጥ ይጋልባል፡፡በመንፈሳዊያን ስሌት ሰው ሁለቴ ይወለዳል..አንድም ከወላጆቹ በስጋ ..ከዛ ከአምላኩ በመንፈስ…እኔም አሁን ሁለተኛ እንደተወለድኩ እየተሰማኝ ነው.ከትርሲት ንጽህ እና የጠራ ልብ ውስጥ በፍቅር እንደተወለድኩ…፡፡አዎ ለዛ ነው መቼም ተስምቶኝ የማያውቀው ሙሉነት እየተሰማኝ ያለው ፡፡ልክ ንፁህ ዘይት እንደተቀየረለት ሞተር ደሜ በእያንዳንዷ ህብረሰረሰሬ ..በእያንዳንዷ የሰውነቴ ቅንጣ ሲራወጥ እና ሲብላላ ይታወቀኛል፡፡ፍፅም ሰላም እና ፍፅም ጤንነት ይሰማኛል፡፡
እንደተለመደው ዊልቸሬ ላይ ቁጭ ብዬ በፅሞና የጥዋት ፀሀይ እየሞቅኩ ነው..ለስለስ ያለች ስሜት ነዛሪ ሙቀት ያላት ፀሀይ ነች፡፡ሰዓቱ ከጥዋቱ ሶስት ሰዓት አካባቢ ነው፡፡እናቴም መደገፊያ ያለው ደረቅ ወንበር ላይ ከጎኔ ተቀምጣ ትካዜ ይሁን ተመስጦ ባለየውት ዝምታ ውስጥ ተውጣለች..በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ከተቀመጥን አንድ ሰዓት አልፎናል፡፡አንድ ሰዓት በየራሳችን ሀሳብ ውስጥ ተሸሽገን….
ቅድም ሲንጫጩ እና ሲዘምሩ የነበሩት ባለ አስደማሚ ህብረ ቀለም ወፎች አሁን ፀሀዬ ጠንከር እያለች ስትሄድ መሰለኝ አይታዩም…..ግቢ ውስጥ ማንም አይታይም .እቤት ውስጥ ግን የእኔዋን ትርሲትን ጨምሮ ቢያንስ 3 ሴቶች እንዳሉ አውቃለው፡፡ግን አይታዩንም….
ድንገት እናቴ ሰትመጣ ከነበረችበት የደበተ ስሜት እንደመባነን ብላ ታወራኝ ጀመር‹‹…የእኔ ፀጋ ዛሬ የሚገርም ህልም ነው ያየውት…እዚህ እተቀመጥንበት ቦታ ላይ ትልቅ በጥላው ግቢውን የሚያለብስ ዋርካ በቅሎ አየው… ብታይ ሚገርም ዛፍ ነው…እንዴ …?ከየት የመጣ ዛፍ ነው……?ማን ተከለው…..…? መች አደገ ……?ተገርሜ ጠይቃለው ፡፡ሌላ ሰው አጠገቤ ኖሮ ሳይሆን እንዲሁ ከመገረሜ ብዛት ከራሴ ጋር ነበር እያወራው የነበረው..ግን ሌላ የሚያስደምም ነገር አጋጠመኝ..አንድ ፍም የመሰለ ቀይ አዛውንት ..አንደ በረዶ የነጣ ትከሻው ላይ የተንዛፈፈ ሉጫ ፁጉር ያለው መልከ መልካም ብርሀናማ ዓይኖች ያሉት አዛውንት ከላይ ሰማዩን ሰንጥቆ እየተምዘገዘገ መጣና በሁለት ሜትር እርቀት ፊቴ ቆመ‹‹ልጄ ለጥያቄሽ መልስ ልሰጥሽ ነው የመጣውት››
ለየትኛው ጥያቄዬ››ስል መልሼ ጠየቅኩት
‹‹ስለዚሁ ግዙፍ ዛፍ እየጠየቅሽ ስላለው ጥያቄ››
‹‹እሺ እንዴት ሆነ …?ይሄ ዛፍ ከየት መጣ..…?››
‹‹አይ ድሮም የነበረ እኮ ነው… እራስሽ ነሽ ወጣት እያለሽ የተከልሽው…. ግን እስከዛሬ በስህተት ወደ ታች ነበር ሲያድግ የነበረው..››
እና እንዴት በአንዴ ይሄን አክሎ ላየው ቻልኩ…?››
‹‹አሁን የመስተካከያው ጊዜ ስለደረሰ ነው..አየሽ የተጣመመው የሚቃናበት… የተደፋው ሚታፈስበት…የወደቀው የሚነሳበት…የተሰበረው ሚጠገንበት የሄደው ሚመለስበት…የጠፋው ሚገኝበት…የጨለመው ሚነጋበት ለሁሉም የራሱ የሆነ ጊዜ አለው…መሆን የሚገባው ነገር ሁሉ ጊዜውን ጠብቆ መሆኑ የማይቀር ነው…ካልሆነ ደግሞ መጀመሪያውኑ መሆን የማይገባው ነገር ይሆናል…. ስለዚህም ይሄም ዛፍ ወደ ታች ማደጉንና መስፋፋቱን አቁሞ እንዲህ ከመሬት በላይ ግርማ ሞገሱን ጠብቆ ለመታየተ አሁን ጊዜው ስለሆነ ነው ያስተካከልነው…አሁን አንቺም ልጆችሽም በጥላው ትጠለላላችሁ….በውበቱ ትደመማላችሁ….እላዩ ላይ ጎጆቸውን ቀልሰው ዝማሬ በሚዘምሩ አዕዋፋት ትዝናናላችሁ…እላዩ ላይም የንብ ቀፎ ሰቅላችሁ ወለላ የማር እሼት እየቆረጣችሁ ልትመገቡም ትችላላችሁ›› ብሎ አብራራልኝና እንደ ደመና እየተበታተነ ቅርፁን በማጣት ከአየሩ ጋር ተዋሀደ…እና ነቅቼም እንኳን ሽበታሙ አዛውንት ሆነ ግዙፍ ዋርካ ከአዕምሮዬ ሊጠፋ አልቻሉም..እና የዚህ ህልም ፍቺ ጥሩ ይሁን መጥፎ አላውቅም …ግን አንድ ታአምር በቤታችን የሚፈጠር ይመስለኛል..አዎ በዛ እርግጠኛ…..
ሀርሜ-ኮ ንግግሯን ሳትጨርስ የውጩ በራፍ ተንኳኳ… ሀርሜ ወሬዋን አቆርጣ እንደመባነን አለችና በዝግታ ከተቀመጠችበት ወንበር በመነሳት ቆመች….እግሯን አፍታታች….ሳስበው የደነዘዛት ይመሰለኛል፡፡በእርጋታ ወደ በራፉ ስትሄድ እያየዋት ነው ..ደረሰችና የወጩን በራፍ ከፈተች…..ገርበብ አድርጋ በልኩ…. ወዲያው ግን ሊገመት በማይችል የድንጋጤ ይሁን የፍራቻ ስሜት ድምጽ አውጥታ በመጮህ መልሳ በራፉን ደረገመችው…አይኖቾ በድንጋጤ ተበለቀጡ… እንዴ ምን ነካት..?እብድ ነው እንዴ በራፉን ያንኳኳው?››እራሴን ጠየቅኩ..
ሀርሜ በራፉን ቀርቅራ ተደግፋዋለች .. በድንጋጤ እየተንቀተቀጠች ያለችም ይመስለኛል….እጆቾን አፏ ላይ ከድናለች….አሁንም በራፉ መንኳኳቱን ቀጠለ…..እናቴ የሚያንኳኳው ሰው በራፉን ገንጥሎት ወደ ውስጥ እንዳይገባባት የፈራች ይመስል በራፍን መልሳ ዘግታ እላው ላይ በሙሉ ኃይሏ በመደገፍ ወጥራ ይዘዋለች..በዚህ ጊዜ ከኃላ ድምጽ ተሰማኝ…‹‹እንዴ እማ ማነው?››የሮሚ ድምጽ ነው፡፡….ከቤት ወጥታ እናቴ ወዳለችበት እየተጠጋች…
‹‹ እማ ምን ሆንሽ..?ማን ነው የሚያንኳኳው…?.››ከሀርሜ መልስ የለም…
‹‹ብቻ ፃረ-ሞት ያየ ሰው መስላለች››….ከውጭ ማንኳኳቱ ቀጥሎል…
ሮሚ ሀርሜ ያለችበት ቦታ ደረሰች‹‹እማ !!እስቲ ዞር በይ… ማን ነው…?››
‹‹ተይ ልጄ ተይ….ማንም አይደለ››በራፍ እንዳይከፈት አጥብቃ ተከላከለች
‹‹እንዴ እየተንኳኳ ?እይሰማሽም .. …?››
‹‹ተይ ይቅርብሽ ልጄ››ተማፀነቻት
ሮሚ ለደቂቃዎች የእናቷን ጤንነት የተጠረጠረች ይመስለኛል .አዎ አስተያቷ እንደዛ ነው ሚመስለው..እናቴን አፍጥጣ አየቻትና እንደምንም ጎትታ ከበራፍ ላይ ዞር አደርጋት…. በራፉን በከፊል ከፈተችው
ጤነኛ ሰው ነው የሚታየኝ …. ፀዳ ያለ ልብስ የለበሰ…የተመቸው አይነት ሰው
እሮማን የከፈተችውን በር በአንድ እጆ እንደያዘች ‹‹አቤት ምን ነበር…?››ብላ ፊት ለፊቷ ያለውን ሰው ጠየቀችው. ሰውዬው እንደእናቴ ፈዟል..ድንገት የህይወቱ ህልም የሆነችውን ልጅ መንገድ ላይ አይቶ በፍቅር እንደነሆለለ እርብትብት ጓረምሳ ሮሚ ላይ አፍጥጦባታል…
‹‹አቤት !!!ማንን ፈልገው ነው…?››ደግማ ጠየቀችው
‹‹እርግቤ…በጣም አድ…ገ….ሻል..ትልቅ ልጅ ሆነሻል››
‹‹ዋት….እርግቤ…››በታላቅ መገረም መልሳ ጠየቀችው
በዚህ ጊዜ የእኔም ሰውነት መንቀጥቀጥ ጀመረ..አዎ ሮሚን እርግቤ ብሎ ይጠራት የነበረው አንድ ሰው ነው..ሮሚን ብቻ ሳይሆን ፌናንንም በተመሳሳይ ስም…ሁለቱ አንድ ላይ ሲሆኑ ደግሞ እርግቦቼ ይላቸው ነበር…. ይሄንን ታሪክ በተደጋጋሚ ጊዜ ሰምቼዋለው ከእናቴ ሰምቼዋለው‹‹..ሰውዬው መጣ ማለት ነው……?አሁን የእናቴ የድንዛዜ ምክንያት በግልጽ ፍንትው ብሎ ገባኝ….
‹‹አባዬ..››ሮማን እጆቾን በድንግጤ ጭንቅላቷ ላይ ጭና…
‹‹አዎ አባትሽ ነኝ..ልጄ››ዘላ ተጠመጠመችበት…ወገቧን አቅፎ በአየር ላይ አሽከረከራት…ፀጉሯ በንፋሱ ብትንትን አለ ከውጭ ለሚታዘባቸው በፊልም ላይ ደገግመን የምናያቸው ሮማንቲክ ፊልሞች ላይ የሚሰሩ ፍቅረኛሞች ይመስላሉ..አንገቷ ስር ገብቶ ሲስማት ይታየኛል..አዎ እያለቀሰም መሰለኝ..እሷም እያለቀሰች ነው..እናቴ ደንዝዛ ከቆመችበት ቦታ በደመነፍስ ለቃ ወደእኔ መራመድ ጀመረች …አዎ ፊቷ ግርጥት ብሏል..ሰው እንዴት በደቂቃ እንዲህ ቅይርይር ይላል…?፡፡ሰሬ ደረሰችና ቅድም ተቀምጣበት የነበረበት ወንበር ላይ ተቀመጠችና በጣም በደከመ እና በሰነፈ ድምፅ ‹‹አባትህ መጥቷል›› በአለችኝ
አይኔን በንዴት እና በጥላቻ አጉረጠረጥኩት….ሮሚ ገረመችኝ..ልክ ለአንድ ሳምንተ ለቫኬሽን
👍10
ወደ ዱባይ ወጣ ብሎ ስጦታ ይዞላት የተመለሰ አባቷን ያገኘች ቀበጥ የቦሌ ወጣት ትመስላለች..እንዴት በሽርፍራፊ ሰከንድ ያንን ሁሉ አመት ጥሏት ያለአባት እየተሳቀቀች እንድታድግ የፈረደባትን ሰው አባት ብላ ይቅር ማለት ቻለች……?እንዴት አይነት ጅልነት ነው…. …?በምወዳት እህቴ ክፉኛ ተበሳጨውባት..እንዲህ አቋም የሌላት ወረተኛ መሆኖን አስቤውም አላውቅም ነበር
ሰውዬውን ወደግቢው ውስጥ ይዛው ስትገባ ከኃላቸው አንድ ሌላ ሰው ተከተሏቸዋል…አይ ሌላ ሰው አይደለም የእኔው ጉድ ነው ..የገዛ ወንድሜ …፡፡ወደቤት ይዞት የመጣው እሱ መሆኑን ሳውቅ ደግሞ ገረሜታዬ በእጥፍ ጨመረ…እንዴ ይሄን ሰውዬ እኔ ብቻ ነኝ እንዴ የምጠላው…? ››
ተያይዘው እኛ ወዳለንበት መጡ …ሀርሜ ጋር ሲደርሱ ሶስቱም ቆሙ…ያንን ክፉ ሰውዬ እንደመንግስት ባለስልጣን ሁለት የምወዳቸው ወንድምና እህቶቼ ከግራና ከቀኙ አጅበውታል..ከሁለቱም ፊት ላይ ሳቅ ይፈሳል… ሰውዬው በዛ ዝግባ ቁመቱ ቅንጥስ ብሎ ፊቷ ተደፋ..ጫማዋ ላይ‹‹ይቅር በይኝ..አውቃለው ጥፋቴ ከይቅርታ በላይ ነው…ግን ባክሽ በልጆቻችን ይዤሻለው.. ይቅር በይኝና ቀሪ ዘመኔን ሙሉ አገልጋይሽ ሆኜ ልካስሽ … ››
‹‹ተነስልኝ…ከእግሬ ስር ተነሳልኝ››እናቴ በቁጣ እግሯን መነጨቀችው
‹‹..ይቅር ካላልሺኝ አልነሳም…?››
‹‹በሁሉም ልጆቼ ነፍስ እምልልሀለው…..መጀመሪያ የልጄን ይቅርታ እስካላገኘህ ድረስ ፈፅሞ ይቅር ልልህ አልችልም….ከማናችንም በላይ የበደልከው ፀግሽን ነው…እሱ ይቅር ያለህ ቀን እኔም ይቅር እልሀለው››ፍርጥም ብላ የመጨረሻ የሚመስለውን ውሳኔዋን አሳወቀችው፡፡
እሱም‹‹እሺ እሺ እያለ…›› ከተቀመጠበት ተነሳና ወደ እኔ መጥቶ በርከክ አለ…‹‹ …..ልጄ አንተን ይቅርታ ለመጠየቅ በጣም ነው የማፍረው… እባክህ…››እያለ እጁን ዊልቸሩን መከታ አድርጎ የተቀመጠው በድን የእግሬ ታፋ ላይ አስቀመጠ…እጁን ሰውነቴ ላይ ሲያሳረፍ ልቆጣጠረው የማልችል የሆነ የሚነድ እሳት በሰውነቴ ተንቀለቀለ…ከእሳት ያለፈ እሳተ ጎመራ …. ባላሰብኩትና ከቁጥጥሬ ውጭ በሆነ ኃይል መንጭቄ እጁን ከእግሬ ላይ በማንሳት አሽቀነጠርኩለት..በድንጋጤ በተቀመጠበት ክንብል ብሎ ወደ ኃላው ተዘርጥጦ ወደቀ…ግን ያላሰብኩት ነገር ተከሰተ..ሀርሜ ምንጩ ባልታወቀ እልልታ ግቢውን አደበላለቀችው…. ከተቀመጠችበት መቀመጫ ተነሳችና ተጠመጠመችብኝ… አገላብጣ ትስመኝ ጀመር ..ግራ ገባኝ… ምን አይነት የእብድ ቀን ነው……? ምንድነው እንዲህ በአንዴ ከሀዘን ውስጥ መንጭቆ የደስታ ባህር ውስጥ ያንቦራጨቃት……? ምን ተከሰተ..…?የድሮ ፍቅሯን ማየቷ ቀልቧን እንደመንሳት አደረጋት እንዴ..…?
‹‹ወይኔ እግዚያብሔር ..ወይኔ ፈጣሪ …. ሰውዬውን ያመናጨቅኩበትን እጄን ያዘችና ወደ ከንፈሯ ወስዳ ትሰመው ..ትሰመው ብቻ ሳይሆን ትልሰውና እጣቶቼን በየተራ ትመጣቸው ጀመር..‹‹አጃኢባ ረቢ!!!››ይላሉ የእናቴ ዘመዶች እንዲህ አይነት መላ ቅጡ የጠፋ ነገር ሲያጋጥማቸው… እኔም በዛው እጄ ከጉንጮቾ ላይ የሚወርደውን እንባዋን አብስላት ጀመር
‹‹አያችሁልኝ..አያችሁ የፈጣሪን ስራ…?››
‹‹እንዴ እማ ..ሰላም ነሽ ግን…? ››ሮሚ የሁሉንም ግራ መጋባት ወክላ ጥያቄዋን አቀረበች
‹‹በጣም እንጂ..የልጄ ሌለኛው እጅ እኮ ነው የተንቀሳቀሰው..ልጄ እየዳነልኝ ነው››
ሀርሜ የምትናገረውን እንኳን ሌሎች ለእኔም በትክክል አልገባኝም…ጉንጯ ላይ እንባዋን የሚጠርገውን እጄን አስተዋልኩት…መብረቅ የመታው ግንድ ይመስል ከመገረም በመጣ ድንጋጤ ውስጤ ተፈረካከሰ… ቀኝ እጄ ነው.. አላምን ብዬ ግራዬን አየውት እሱም ይንቀሳቀሳል…አዎ ሀርሜ ትክክል ነች…ሁለቱም እጄ መንቀሳቀስ ጀምሯል…ወይኔ ሁለቱም እጄ ተንቀሳቀሰልኝ..ግቢው በእልልታ እና በጩኸት ተደበላለቀ….እቤት ቀርተው የነበሩት እነትርሲትም መጥተው ተቀላቀሉን… ሁሉም ትንፋሽ እስኪያጥረኝ ዙያዬን ከበው ያቅፍኝ ና ይስሙኝ ጀመር….
እናንተዬ… ይሄ ሁሉ 30 በማይሞሉ ደቂቆች የተከሰተው ትርምስምስ ተዓምራዊ ድርጊት የእናቴ የለሊት ህልም ፍቺ ይሆን እንዴ …….…?

💫ይቀጥላል💫

Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍7
#አቤቱ_አሁን_አድን
:
ከለምለም ሳር እንዳትቀምስ
ከመስክ ወጥታ እንዳትበላ
ባውቅልህ ባይ ጌቶቿ ~ ለዘመናት ተከልክላ
ከ'ስር ቤቱ ለታጎረች ~ በጠባብ ቤት ተከልላ
ውሀ ጥሙ ላደረቃት ~ ላህዪቷ ውርንጭላ
የነቢያት ትንቢታቸው ~ የመዳን ቀን ደረሰላት
መፈታቷ እውን ሆነ ~ ነፃነቷም ሰመረላት
እሰይ!
:
ጌታ ሆይ ..
ዛሬም ድረስ እስ'ራቱ ~ መታረዙ አቁስሎናል
አ'ጥያታችን ከርፍቶ ~ ከትቢያው ላይ ጥሎናል
ከመከራው ከመቅሰፍቱ
ከሰቆቃው ከመኃቱ
ከርግማኑ ሜዳ ላይ ~ አቅም አጥተን ወድቀናል
.
.
ትሁቴ ሆይ!
ፃድቄ ሆይ!
የተናቀን የምታከብር ~ የወደቀን ምታ'ነሳ
በ'አህያይቱ ግል'ገል ~ በ'ተናቀችዋ እንስሳ
በውርንጭላ ተጭነህ ~ ወደ ልባችን አቅና
በምህረትህም ጎብኘን ~ እንበልህ ሆሳህና
:
:
🌿🌿 መልካም የሆሳህና በዓል .. !!🌿🌿
#ሀርሜ_ኮ
:
ክፍል-ዘጠኝ

:
:
ደራሲ- ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

...ሳምንት ቢያልፈውም የተአምራዊው ቀን አንጎበር ዛሬም ድረስ ከቤታችን
አልጠፋም…አብላጫውን ደስታ ነው..ሳቅና ፈንጠዝያ ነው..ይሔ ደስታ ደግሞ
በእኔ አካል ላይ የታየ አዲስ ለውጥን ተከትሎ የተከሰተ ነው..የቀኝ እጄ
ለአእምሮዬ መታዘዙን ተከትሎ…ይሄ ማለት ምን ያህል ከባድና ሊታመን
የማይችል ተአምራዊ ክስተት መሆኑን የምናውቀው እኔና ቤተሰቦቼ ብቻ ነን…
መከራውን ለሃያ ምናመምን አመት ተሸክመን የኖርነው፡፡ደግሞ ሌላም
አስተውለን የማናውቀው ግን ቀን በቀን ኢምንት ያህል ለውጥ እያሳየ የነበረ
የአካሌ ክፍል እንዳለ መረዳት ችያለው..የአንገቴ ነገር..፡፡አንገቴ እንደ ድሮው ወደ
ዞረበት ክንብል ብሎ የሚደፋ አቅመቢስ አይደለም…ከአንዱ አቅጣጫ ወደ
ሌላው አቅጣጫ ለመዞር የሚፈጅበት የጊዜ ስሌት በ50 ፐርሰንት ማፍጠን
ችሏል፡፡ ይሄም ድንቅ ነው…..ዘንድሮ እኔን በተመለከተ መንገዶች ሁሉ ወደ ተስፋ እያመሩ
ያሉ ይመስለኛል..ደግሞም እንደዛ ነው….፡፡
ሌላው ከደስታችን ጋር የተቀየጠ የሆነ የታፈነ ጭንቀትም በቤታችን አለ …
ሰውዬውን በተመለከተ አሁንም ደጅ እንደፀና ነው…፡፡ልጆቹን በጠቅላላ ማሳመን
እና ከጎኑ ማሰለፍ ችሏል..፡፡ለዛውም በቀላሉ..፡፡ሌላው ይቅረ መፈጠሩንም
የማታውቀው ትንሻ ማክዳ እንኳን እላዩ ላይ ስትንጠለጠል ሳይ በግርምት አፌን
እይዛለው…እስከአሁን እኔና እናቴን ነው ያልቻለው…እናቴ አንዴ የሰጠችውን ቃል
ልትቀይር ፍቃደኛ አይደለችም…ጉዳዩን ወደ እኔ መርታዋለች..እኔ ደግሞ አይኑን
ሳይ እራሱ ያቅለሸልሸኛል…ሲሸማቀቅ ሳይ ውስጤ ይረካል….
አሁን መኝታ ቤቴ ተኝቼ ስለዚሁ ጉዳይ እያሰላሰልኩ ሳለው በሩ በስሱ ተንኳኳና
ተከፈተ‹‹ይህቺ እብድ ልትሸውደኝ ነው ..ብዬ አንገቴን ወደ በሩ አዞርኩ..ትርሲት
መስላኝ ነበር፣ግን አይደለችም ፤ወንድሜ ነው
‹‹…ይቅርታ አረበሽኩህም አይደል?››እያለ ወደ እኔ መጣና አልጋው ጠርዝ ላይ
ተቀመጠ…….
‹‹ወንድሜ አንድ ነገር ላወራህ ፈልጌ ነው…››አይኔን በማርገብገብ እንዲቀጥል
አበረታታውት
‹‹ስለአባቴ ነው ላወራህ….››ንግግሩን ሳይጨርስ እጄን አፉ ላይ ከደንኩበት…
በዚህ ርዕስ ላይ ከማንም ጋር ማውራት እንደማልፈልግ በደንብ እንዲያውቅ
ስለፈለግኩ
እሱም እጄን ከአፉ ላይ አንስቶ ወደ ቦታው በመመለስ ንግግሩን
ቀጠለ‹‹..ወንድሜ የምትወደኝ ከሆነ የግድ ልታዳምጠኝ ይገባል..እምልልሀለው
ዛሬ ለመጨረሻ ጊዜ ነው የማናግርህ..የምወድህ ታላቅ ወንድሜ ነህ ስለዚህ
ባትወደውም እንድታዳምጠኝ እፈልጋለው..ውስጤ ያለውን ስሜት ለመጨረሻ
ጊዜ አውጥቼ ልነግርህ እፈልጋለው…ምንም እንድታደርግ አልፈልግም
እንድታዳምጠኝ ብቻ ነው የምፈልገው……››
ምንም ማድረግ አልቻልኩም …ይሄንን ተማፅኖውን አሻፈረኝ ልለው አልችልም
ስለዚህ ቢጓመዝዘኝም ተረጋግቼ ላዳምጠው ወሰንኩ …..
‹‹እሺ ሳለፈቀድክልኝ አመሰግናለው..ፀግሽ ምን መሰለህ…እርግጥ አንተ ምን
እንደሚሰማህ አውቃለው …በእሱ ምክንያት ከሁላችንም በላይ ያንተ ልብ ነው
የቆሰለው…በአንተ ምክንያት ነው ፍቅሩንም ቤቱንም ልጆቹንም ጥሎ
የሄደው…..ይሄ ደግሞ እሱን ለመጥላት እሱን ይቅር ላለማለት ከበቂ በላይ
ምክንያት ነው..ግን ምን መሰለህ አሁን ስለእሱ እኔን ብትጠይቀኝ ምንም እንኳን
በዛን ወቅት የሰራውን ታሪክ ሳስታውስ በጣም ብረበሽና ቅሬታ የሚሰማኝ
ቢሆንም በጥላቻ የተጋረደ እይታ ግን የለኝም፡፡አውለው…ይሄ ቤተሰብ በጣም
ብዙ መከራ አሳልፎል…በተለይ እናታችን ይሄን ሁሉ ልጅ ለብቻዋ አባትም እናትም
ሆነ አሳድጋለች…ግን ቢሆንም ያው ጉድለቱን ሙሉ በሙሉ ልታጠፋው አልቻለችም…
አንዳንዴ አባት እና እናት ከልጆቻቸው ጋር ያላቸው ግንኑነት ከሆነ ነገር ጋር
የተገናኘ አይመስለኝም…ማለቴ ከእነሱ ጥሩነት እና መጥፎነት ጋር… ከእነሱ
ሀብታም መሆንና ድህነት ጋር….ከእነሱ የትምህርት ደረጃቸው ጋር አዎ ከእነዚህ
ሁሉ ነገር ጋር የተገናኘ አይደለም..ዝም ብሎ ምከንያት አልባ ነው… ተፈጥሮዊው
ብቻ…በደም ትስስር እና በነፍስ ቁርኝት የተገመደ ዝም ብለህ የምትቀበለው
ሚስጥራዊ ጥምረት ነው..ለዛ ነው ሁለችንም ሳናስበው በዚህ ፍጥነት
የተቀበልነው…በዚህ ፍጥነት ይቅር ያልነው..፡፡
ካንተ በስተቀር ሁላችንም ጋር ያለው ስሜት ተመሳሳይ ነው..እርግጥ የእኛን ካንተ
ጋር ማወዳደራችን አይደለም …ግን ያው አባትነቱ ለሁላችንም እኩል ነው…አየህ
አሁን እሱን ይቅር ብለነው ወደ ህይወታችን እንዲቀላቀል ካልፈቀድንለት
ወደፊትም ባለው ሙሉ ህይወታችን ስለአባት ያለን ትዝታ ባዶና ጥቁር ብቻ
ሊሆን ነው…ለልጆቻችንስ ምን እንነግራቸዋለን….?ስለአባታችን ሲጠይቁን
ምንም የምንላቸው ነገር አይኖረንም..ይሄ ቀላል ይመስልሀል ?›››
ቀኝ እጅን ከግራ ወደ ቀኝ በማወናጨፍ ፈጽሞ ይቅር ልለው እንደማልችል ደግሜ
አስረዳውት
እሱም የማሳመን ጥረቱን ቀጠለ‹‹አይ እኔ ምንም እንድትለኝ አልፈልግም….
ስለውሳኔህ እንድትነግረኝ አልፈልግም…እኔ እንዳልኩህ የውስጤን ነግሬህ ብቻ
መሄድ ነው የምፈልገው…..
አየህ አብዛኛውን ነገር ነግሬሀለው ግን አንድ ነገር ይቀረኛል..እናቴን በተመለከተ
..እናቴ እሱ ላይ እርግጠኛ ሁን ጥላቻ የላትም..ያን ያህል ቢበድላትም ግን
አሁንም ይቅር ልትለው ትፈልጋለች..እንደውም በውስጧ ድሮ ገና ድሮ ይቅር
ያለችው ይመስለኛል..አሁን እሷ ላይ የሚታው ንዴት ነው…ከፍተኛ ንዴት…አየህ
ቅድም እንደነገርኩህ ከሁላችንም በላይ አንተን ጎድተቶሀል አቁስሎሀል..ግን ያ
እውነት የሚሆነው ከእኛ ከልጆቹ ጋር ሲነፃጸር ብቻ ነው..ከእናታችን ጋር ሲነፃፀር
ግን በአንተ ላይ ያደረሰው በደል ትንሽ ነው…አየህ ፍቅሯን ነው የነጠቃት… አራት
ልጆቾን ነው ብቻዋን እንድታሳድግ በትኖባት የሄደው..ያለ ባል ነው ይሄን ሁሉ
አመት እንድትኖር የፈረደባት…ሌላ ወንድ ላፍቅር ብትል እንኳን አትችልም.. ማን
ነው አራት ልጆች ያሏትን ሴት ሚስቴ ብሎ የሚቀበለው..
..አልፎ አልፎ ነበር የእሱ አለመኖር በውስጣችን የፈጠረው ሽንቁር
የሚታወቀን፣ምክንያም እሷ ለደስታችን በየእለቱ ትፈለምልን ነበር …ለሳቃችን
በየደቂቃው ትዋደቅልን ነበር…ሀዘኑን ሁሉ ለብቻዋ ውጣ ወደ እኛ እንዳይደርስ
ግድግዳ ሆና ትከላከልልን ነበር….ችግር ወደቤታችን እንዳይገባ በፅናት
ስትታገል ነው የኖረችው…
እሷ ግን ይሄንን ሁሉ አመት በሀዘን እንደተለበለበች ነበር….ግማሽ እድሜዋን
በፍቅር ክህደት የተጎዳ ልቧን እየመረቀዘባት ..ከምርቅዙ የሚመነጨውን መግል
እየጠረገችና እያስታመመች የኖረች ሚስኪን ሴት ነች..ለልጆቾ ስትል መስዋዕት
የሆነች ሴት …በተለይ ለአንተ ስትል መስዋዕት የሆነች ዕንቁ እናት ነች..እና አሁን
እኔ አንተን ብሆን ለእሷ ስል መስዋዕት እሆን ነበር….›› ግራ ጋባኝ አባባሉ እንዴት ነው?እንዴትስ ነው ለእናቴ ስል መስዋዕት ልሆን
የምችለው..?እርግጥ ነው ለእናቴ ጥቂት ደስታ ማምጣት ከቻልኩ ህይወቴን
እንኳን በመስጠት መስዋዕት ለመሆን አላቅማማም ምክንያም ይህ ህይወቴ
ይሄን ሁለ ዘመን በዚህ ምድር የኖረው በእናቴ ብርታትና ጥንካሬ ነው፣..ሀርሜ ኮ
የህልውናዬ መሰረት ሁሉ ነገሬ ነች…
ወንድሜ ቀጥሏል‹‹አየህ ከልብህ እንኳዋን ባይሆን አባትህን ይቅር ብትለው
ለእናታችን ትልቅ ነገር ይመስለኛል አየህ አንተ ይቅር ማለትህን ካወቀች እሷም
ይቅር ማለት አይከብዳትም ያንን ደግሞ እንደምታደርግ በቃሏ
አረጋግጣልናለች አንተ ከእሱ ጋር መቀራረብ ብትጀምር እሷም ሁሉን ነገር ረስታ
እንደአዲስ ትቀርበዋለች..እና ደግሞ በሂደት አንተ ከእሱ ጋር አንድ ላይ መኖር ብትፈቅድ
👍31
እርግጠኛ ነኝ እሷም በደስታ ታደርገዋለች...አየህ እንዴት እንደሚሆን
…ለእናቴ ደስታዋን መመለስ ምትችለው አንተ ነህ…ለእናቴ ከዘመናት በፊት
የቆሰለ ልቧ እንዲጠገን መንገዱን ማመቻቸት የምትችለው አንተ ብቻ ነህ…
እናቴን ዳግመኛ መዳር የምትችለው አንተ ብቻ ነህ..ግን ይሄንን የግድ ማድረግ
የለብህም የምታደርገው ከፈለግክና ውስጥህ በትክክል ከተቀበለው ብቻ
ነው...በል ይበቃኛል ..ይሄንን ብቻ ልልህ ነው የመጣውት አለና ከተቀመጠበት
ተነስቶ በፍቅር ግንባሬን ስሞ እኔን በውጥረት ለተሞላ ሀሳብ ውስጥ ሰንቅሮኝ
ጥሎኝ ሄደ
እሱ ከሄደ ቡኃላ ለረጅም ስዓት በፍዘት አሰብኩበት ..በመጨረሻ ግን ወንድሜ
የተናገረው ሁሉ በጣም ትክክል ሆኖ ነው ያገኘውት…ታናሽ ወንድሜ ቢሆንም
ከእኔ በጣም የተሸለ ነገር ማሰብ በመቻሉ ኮርቼበታለው..እኔ ይሄን ጉዳይ
በተመለከተ እራስ ወዳድ እየሆንኩ እንደሆነ እንዲሰማኝ አድርጎል ..አባቴን ይቅር
ማለት እና አለማለት ከእኔ ፍላጎት አንጻር ብቻ ነው ያየውት ..የእኔ ከእሱ ጋር
ሰላም አለመፍጠር ወንድሜንና እህቶቼን እንደሚረብሽ አስቤው አላውቀውም
ነበር..ከሁሉም በላይ ከእናቴ አንጻር ማሰብ ነበረብኝ….ሰሞኑን አይኖቾ ውስጥ
ለጣር የቀረበ ስቃይ አንብቤለው….. ስትፈዝና በተቀመጠችበት ስትደነዝዝ
በተደጋጋሚ ጊዜ መታዘብ ችያለው…አዎ እርግጠኛ ነኝ ወንድሜ እንዳለው
ሰውዬውን ቀድማ ይቅር ብላዋለች..እንደውም የናፈቃት ሁሉ ይመስለኛል…
ልታወራው የጓጓች ..ብዙ ብዙ ጥያቄዎች ልትጠይቀው ፈለገች…..እና
ልታቅፈውና ልትስመው የምታልም..ግን እኔ በብረት እና በአርማታ ተቀይጦ
የተሰራ ጥብቅ ግድግዳ ሆኜባታለው..አዎ በመሀከላቸው የተደነቀርኩት ጋሬጣ
እኔ ነኝ፡፡ እድሜ ለወንድሜ አሁን ሁሉ ነገር ፍንትው ብሎ ተገልፆልኛል……ስለዚህ
ይሄን ሰውዬ ባልወድም ይቅር ልለው የግድ ነው..ለእናቴ ስል ..፡፡ደግሞ እንደዛ
ማድረጌ ለራሴም ጤና ጥቅም ይኖወረዋል መቼስ ጥላቻና ቂም አፍራሽ
ስሜቶች ናቸው ..በውስጤ ያለውን ፍቅር እና ተስፋ ያጨለሙታል እንጂ ሌላ
እርባን አይኖራቸውም …ስለዚህ እጄን ጎኔ ወዳለው ኮመድኔ ላኩና እስኪሬብቶና
ወረቀት ስቤ አነሳው…
‹‹ሰውዬውን ላገኘው ፈልጋለው››ብዬ ጻፍኩና ራስጌዬ ያለውን መጥሬያ
ተጫንኩት… በሁለት ደቂቃ ውስጥ ትርሲቴ እየበረረች መጣች
‹‹ወይኔ ፍቅር ረሳውህ አይደል? ማዕድ-ቤት ስራ ይዤ እኮ ነው..ልጅቷን
እያገዝኮት ነው..ትንሽ ነው ቀረኝ ከዛ መጣና ዘና እንላለን…››
የእሷን ንግግር ችላ ብዬ ወረቀቱን አቀበልኮት…ተቀበለቺኝና አነበበችው‹‹የቱን
ሰውዬ..?አባትህን?››
ግንባሬን በመነቅነቅ እሱን መሆኑን አረጋገጥኩላት
ተንደርድራ መጥታ ከንፈሬ ላይ ተጣበቀችብኝ..ይህ ተለመደ ተግባሯ ከሆነ ቆየ…
እኔ ከንፈር ላይ ለመጣበቅ ምክንያት ነው የምትፈልገው…..እኔም ሁሌ መሳም
ስፈልግ የሆነ ምክንያት ሰጣታለው
‹‹የእኔ ጀግን በጣም ነው ያስደስትከኝ…ውይ እህቶችህ ይሄን ሲሰሙ እንዴት
እንደሚደሰቱ አትጠይቀኝ …ጥዋት ቁርስ ላይ ሁሉም ተጨንቀው ሲላቀሱ
ነበር..ከአንተ ይሁኑ ከአባታቸው አጣብቂኝ ውስጥ ነው የከተትካቸው..ቆይ ይሄንን
ዜና አሁኑኑ ላብስራቸው›› በለማለት ተንደርድራ በሩጫ ወጥታ ሄደች እኔም የሆነ እፎይታ ተሰማኝ.

💫ይቀጥላል💫

Like👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ

አስተያየታችሁን በ @atronosebot አድርሱን
👍7
#ያንቺ_ፍቅር_ሰይጣን

#ያንቺ_ፍቅር_ሰይጣን
ካህን የማይፈራ
ፅናፅል ስዕሉን
ቀርቦ ያናናቀ
ያደረገ ተራ

#ያንቺ_ፍቅር_ሰይጣን
ቁርባን አስደንግጦት
ታቦት ያላራደው
የመንፈስ ነበልባል
የመንፈስ እሳቱ…
ስሜት የማይሰጠው

#ያንቺ_ፍቅር_ሰይጣን
በክፋት ተስሎ ፥ በስሎ የመጠቀ፤
በፀበል ፣ በፀሎት ፥ ቦታ ያለቀቀ።

#ያንቺ_ፍቅር_ሰይጣን
ዓይን የሚሰውር ፥ እንስት የሚጋርድ፤
ካንቺ ገላ ውጪ ፥ ሌላ ‘ማያስወድድ።
.
#ያንቺ_ፍቅር_ሰይጣን
ሀሳብ የሚሰልብ ፥ የመንፈስ ጠበኛ፤
በቅናት ጠፍሮ ፥ ሌት ‘ማያስተኛ።
.
#ያንቺ_ፍቅር_ሰይጣን
ደቁኖ የቀሰሰ!
ከሰዋራ ገዳም…
ዓለም በቃኝ ብሎ
ሙቶ የመነኮሰ።
.
#ያንቺ_ፍቅር_ሰይጣን
ይለቅ እንደሁ ብለው….
እምነት እየቀቡ ፥ በላይ ቢለውሱት፤
ሰይፈ ሚካኤል ፥ ተዓምረ ማርያም፤
እያነባነቡ ፥ በሽብር ቢያምሱት፤
እጣን አጫጭሰው ፥ ዜማ እያወረዱ፤
ቅዳሴ ቀድሰው!
ከበሮ ደልቀው !
ልቡንም ቢያርዱ ...............
“እንቢኝ ፥ አሻፈረኝ”! አለቅም እያለ፤
እንዲያ እንዳልተኩራራ……
እንዲያ እንዳልፎከረ ……….

አንቺን ከሌላ ሰው ፥ ያየሽ ‘ለት ደንብሮ፤
እኔን ለቆ ጠፋ ፥ ቀድሞ ከቀጠሮ ።

🔘ሚካኤል አስጨናቂ🔘
👍4
#ሀርሜ_ኮ
:
ክፍል-አስር

:
:
ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

....ትርሲት ‹‹ሰውዬውን ማናገር ፈልጋለው ››የምትለዋን ወረቀት እንደሰጠዋትን
ወረቀቱን አንጠልጥላ ከመኘታ ቤታችን እየጮኸች ስትወጣ እኔ ግን በውስጤ
መራገም ጀምሬ ነበር..ምን አለ አሁን የሆነ ተአምር ቢፈጠር …ምን አለ አሁን
ይሄንን ሰውዬ ፊቴ ከመቀረብ በፊት እነዛ ማሰር የሚወዱት ሰዎች አንጠልጥለው
ማአከላዊ ወይም ቂሊንጦ ቢወረውሩልኝ፡፡እወነቴን ነው እዛ ባህር ማዶ ሆኖ
ከስልጣን ልቀቁ..ሀገር አትዝረፉ… ህዝብ አታስለቅሱ እያለ በየሶሻል ሚዲያው
ሲዘበዝብ አይደለ የኖረው… እርግጥ አውቃለው በየፌስብኩ ላይ በፅሁፍ
ከመዋጋት ያለፈ ሌላ መሬት የወረደ የትግል ታሪክ እንደሌለው አውቃለው..ይሄ
ታዲያ ሀሳብን በነጻ የመግለፅ ህገ -መንግስታዊ መብቱ ነው ልትሉኝ
ትችላላችሁ…ግን እኮ አሁን እስር ቤቱን በከፊል የሞሉት እኮ ይሄንን ህገ
መንግስታዊ መብታቸውን ሲጠቀሙ የነበሩ ግን በፀረ-ሽብር ህጉ የተጠለፍ
ናቸው ..እና በነካ እጃቸው ይሄን ሰውዬም ቢጠልፉልኝ እፎይ እል አልነበር…?
ለማንኛውም ሀሳቤን ሳልቋጭ ነው መአት የእግር ኮቴ ከወደ ሳሎን አካባቢ ወደ
እኔ ሲርመሰመስ የተሰማኝ..አንዷ በአንዷ ላይ እየተተረማመሱ ወደ እኔ ክፍል
ገቡና ወረሩኝ …ሮሚ.. ማክዳ..ትርሲት ‹‹‹ፀግሽ አሪፍ ውሳኔ ነው…ደስ ብሎናል…
>>አንዷ በቀኝ አንዷ በግራ አልጋው ላይ በመውጣት ጉንጬን አጣብቀው
ይሱሙኝ ጀመር ….ሁለቱ እህቶቼ ሲስሙኝ ፊት ለፊቴ የቆመችው ትርሲት
በመጎምዠት የገዛ ከንፈሩን በስሜት ስትስም ሾፍኮት ...... እናም ታዘብኮትና
ፈገግ አልኩ ‹‹ይሄ ጉድ ደስታ እንደአዲስ አስደመመኝ .… በቃ ይሄ ሰውዬ የቤቱን
ልብ ሁሉ በቀላሉ ተቆጣጥሮታል ማለት ነው…ግን እሱ የሰራውን በደል የሰራ
አንድ ጭርቁስቁስ ያለ አባት ሆኖ ከደንበጫ ወይም ከአሶሳ መጥቶ ቢሆን
እንዲህ ሰፍ ብለው ይቀበሉታል……?እኔ እንጃ ጥርጣሬ አለኝ ..!!አዎ አሁን አባት
ብቻ ስለሆነም አይመስለኝም ዲያስፖራ ነው… ወደ ቤታችን ሲመጣ እራሱ ይዞት
የሚመጣት መሃና ታፈዛለች፡፡
ከግርግሩ ቡኃላ ሁሉም ጥለውኝ ወጡ…በቤቱ ተተረማምሶል ..… በቃ ሰርግ
በሉት የሰርግ ዝግጅት…ትርሲት ወደ መኝታ ክፍል መጣችና ‹‹በል ተነስ ሻወር
እንወሰድ›› ብላኝ እየረዳችኝ ወደ ዊልቸሩ አሸጋገርኩ..አሁን ከአልጋዬ ወደ
ዊልቸሬ መሸጋገር በዙም ከባድ አይደለም..ሁለቱንም እጆቼን በትክክል
መጠቀም ስለጀመርኩ ጥቂት እገዛ ብቻ ነው የምፈልገው ..ደገፋችኝ እና
ከዊልቸሬ ወደ ሻውሩ መቀመጫ አጋላበጠችኝ…እንደገባን ዘጋችው ….
እንደዘጋቻም ቀድማ የራሷን ልብስ ውልቅልቅ አደረገች ፣..ሳቅኩባት ‹‹ምን
ያስቅሀል..…?ምን ሚያስቅ ነገር አለ …?ይሄን የመሰለ ውብ ገላ ያስጎመዣል
እንጂ ምኑ ያስቃል…?›› አለችኝ ሌጣ መቀመጫዋን ፊቴ እያገላበጠች…
እኔ ግን መሳቄን አላቆምኩም …የሳቁኩት እኔን ልጠብህ ብላ ወስዳ ተስገብግባ
የራሷን ልብስ ቀድማ ማውለቋ ነው…. እንጂማ ይሄንን ሰውነት አሁን
ለምጄዋለው… የገዛ የራሴ ሰውነት እስኪመስለኝ እያንዳንዷን ጉብታ፣እያንዳንዷን
ሸለቆ ..እያንዳንዷን ሽፋታ… እያንዳንዷን ጭረት አውቃላው..እንደበቱ የእሷን
እገዛም ሳልፈልግ ከላይ ለብሼ የነበረውን ቲሸርት አወለቅኩት….‹‹ውይ ያንተን
ለካ አለወለቅኩልህም ››አለችን ወደ እኔ ተጠግታ ሱሬዬን እንዳወልቅ
አገዘቺኝ፣አሁን ሁለታችንም ራቁታችንን ነን፡፡ከዊልቸሩ ወደ ሻወሩ አስጠጋቺኝ
‹‹ቆይ መጀመሪያ ከመታጠባችን በፊት ይሄንን የአማዞን ደን የመሰለውን
ጭገርህን ልመንጥርልህ …አለችና የሳሙና ማስቀመጨው ላይ አስቀምጣ
የነበርውን መለጫ ይዛ ፊት ለፊቴ በርከክ አለችና እግሬን ወዲና ወዲያ ከፍታ
ጭኔ መካከል ገባች..እኔም በሁለት እጆቼ ጭኖቾን ፈለቀቅኩና ሸለቆዋን
የከበበውን ጭገር ጨምድጄ በመያዝ እስጮህኮት..‹‹ስለሰው ታወሪያለሽ
የራስሽን እስቲ እይው›› ማለቴ ነው
‹‹አንተ አሳመመምከኝ እኮ… በጣም ባልገሀል ››እያለች ከእጆቼ አላቀቀችና
..ያለችውን ደን በጥንቃቄ መነጠረችው…ወደ ራሷ ስትሸጋገር ጎተትኩና
ተቀበልኮት …..ፊቴ እንድትቆም አድርጌ ልክ ከበድን ድንጋይ ውስጥ ምርጥ
ምስል ጠርቦ እንደሚያወጣ አርቲስት እኔም በፅሞና እና በጥንቃቄ
አፀዳውላት…. ለዛውም ጥበባዊ በሆነ ሁኔታ በልብ ቅርፅ ….እንዴት
እንደምወዳት ለመግለፅ የተጠቀምኩበት ነው…ይህ ደግሞ እንደገመትኩት
እሷንም በጣም ነው ያስደሰታት….ከመደሰቷ የተነሳ የብለቷን ምስል ወዲያውኑ
ነበር በሞባያሏ በማንሳት መልሳ ስታየው ነበረው……ብቻ ከዛ ሻወር ቤት
ለመውጣት አንድ ሰዓት በላይ ነው የወሰደብን….ከዛም ወደ መኝታ ቤታችን
መልሳኝ ዝንጥ ብዬ እንድለብስ አደረገችና ወደ ሳሎን ወሰደችኝ፡፡
የተለመደው ሶፋ ላይ ተመቻችቼ ጋደም አልኩ… ሳሎኑ በምግብ ሽታ ታውዷል፡፡
በራፉ ጥግ ያለ አንድ ገዘፍ ያለ ጠረጰዛ ላይ አስራ ምናምን አይነት ወጣ ወጥ
የያዙ ሰሀኖች ይታየኛል….ሰርግ ያለበት ቤት ነው ያስመሰሉት..ይሄን ሁሉ ምግብ
በዚህ አጭር ጊዜ እንዴት አድርገው ሰሩት በጣም የገረመኝ ነገር ነበር…ደግሞ
አዘናነጣቸው..እሱ ገዝቶላቸው ይሆን …አዳዲስ አይቼ የማላውቀው ልብስ ነው
የለበሱት ከእናቴ በስተቀር..የእኔዋ ትርሲትንም ጭምር፡፡ስድስት ሰዓት ሲሆን
የሳሎኑ በር ተንኳኳ..ሁሉም ለመክፈት ስትራኮት በቆሪጥና በትዝብት እያዋቸው
ነው…ግን ትንhን ማክዳ የቀደማት አልነበረም..ከፍታ መጀመሪያ ያየችው ታናሽ
ወንድሜን ነው …..እሱን ተከትሎ ሰውዬው አለ:: ተጠመጠመችበት ወደ ላይ
አንጠልጥሎ ጉንጮቾን አገላብጦ ከሳማት ቡኃላ መልሶ አስቀመጣት..እንግዲህ
ለእሷ የአባቷንም ቦታ የአያትነቱንም ድርሻ ለመወጣት እየሞከረ መሆኑ ነው፡፡
ከሁሉንም ጋር በመተቃቀፍ ሰላምታ ከተለዋወጠ ቡኃላ እኔና እናቴ ስንቀረው
መሀል ሰሎን ላይ ተገትሮ ቆመ ቁጭ በል ያለውም የለ እሱም ምን ማድረግ
እንዳለበት ግራ የገባው ይመስለኛል፡፡እናቴም በተቀመጠችበት አንዴ እሱን
ደግሞ እኔን እያፈራረቀች ታየኛለች..እህቶቼም ሆኑ ወንድሜ ወደ መሬት
እንዳቀረቀሩ ናቸው…
እንደምንም እግሩን የመጎተት ያህል እያንቀሳቀሰ ወደ እኔ ተጠጋ..በደንብ ተጠጋ
..ከዛ ወለል ላይ በርከክ ብሎ እጁን ወደ ሰውነቴ መዘርጋት ጀምሮ መሀከል ላይ
አቆመው…. የበቀደምለታው ትዕይንት ትዝ ያለው ይመስለኛል..እሱ ብቻ ሳይሆን
እናቴም በተቀመጠችበት ስትሸማቀቅ አየዋትና ሰውዬውን ለማበረታታት ፊቴን
በተጠና ፈገግታ አደመቅኩት…ያልጠበቀው ነገር ነበርና እጁን እጄ ላይ አሳርፎ
ጭንቅላቱን ደረቴ ላይ ደፍቶ
‹‹ልጄ እባክህ ይቅር በለኝ…በቃ በእናት እማፀንሀለው..በእህቶችህና
በወንድምህ እማፀንሀለው..ይቅር በለኝ….፡››ያልቀባጠረው ነገር
የለም….ከንግግሩም በተጨማሪ ከአይኖቹ የሚፈሱት የእንባ እርጠበት ለደረቴ
ደረሰው..ግን አላሰሳዘነኝም..አሁንም አንጀቴ ለእሱ እንደደነደነ ነው…ግን ቢሆንም
ሰላም ለመፍጠር ወስኜያለው እጄን ወደ ግንባሩ ላኩና ቀና አደረግኩት…
ጭንቅላቴን በማነቃነቅ ይቅር እንዳልኩት ሳረጋግጥለት ቤቱ በእህቶቼ የደስታ
እልልታ ተናጋ … ሁሉም እርስ በእርስ መተቃቀፍ ጀመረ››
ሰውዬውም እጆቼን እየሳመ ግንባሬን እየሳመ ‹አመሰግናለው
ልጄ..አመሰግናለው››እያለ ከለበት ተነሳና አቅጣጫውን ቀይሮ ወደ እናቴ
ተስፈነጠረ..እግሯ ስር ከመደፋቱ በፊት ቀልጠፍ ብላ ከመቀመጫዋ ተነሳችና
በአየር ላይ ቀለበችው ተጠመጠመባት ….ተጠመጠመችበት..በቃ ከዚህ
በላይ ያለውን ትዕይንት እናቴን መታዘብ ስለሚሆንብኝ አልነግራችሁም ….

ከሳምንት ቡኋላ
👍9