#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
...በአቅራቢያችን ያለችው ኮክ ለጋ ቅርንጫፎች ደፋ ቀና እያሉ እርስ በእርሳቸው እየተሳሳሙ ይበተናሉ፡፡ ጉንጯ ላይ ሳም ሳደርጋት የፍቅር ደማቅ ችቦ ተሀኮሰ አፌን ወደጎን አንሸራትቼ የከንፈሮቼን ነዲድ ከከንፎሮቿ አርኪ ገለት ጋር በማጋጠም ምጣድና አክንባሉ ሆንን፡፡ በሕሊናችንም ውስጥ ያ የፍቅር ችቦ ፏ ብሎ ሲቀጣጠል ታየኝ።
የወጣትነት ጣዕም፣ የፍቅር ማራኪ ለዛ፣ አንድ የመሆን ፍላጎት በዝግታ ወደ ውስጣችን ሠረፀ፡፡ ሰማይ እንደ አክንባሎ በላያችን ላይ ተደፍታ ቁልቁል ታስተውለናለች። ምን ግዳችን! የሚንቦገቦጉት ክዋክብት በጨለማው ከርስ ውስጥ የሚገኘውን ነገር ሁሉ ብርሃናዊ ውበት ሊዘሩበት ይታገላሉ። እንደ ገና ለስለስ ብሎ ከሚነፍሰው ነፋስ በተገኘው የቅጠላ ቅጠሎች ውዝዋዜ ላይ የከዋክብት ኅብራዊ ቀዝቃዛ ብርሃን ሲያርፍበት በወርቃማ ቀለም የተለበጠ ዕፅኖታዊ ሥዕል ታየ
እኔ በእርሷ የሕይወት ሰበካ፣ እሷም በእኔ የሕይወት መስክ እየተኩነሰነስን ወደማይታይና ወደማይዳስስ የሰመመን ዓለም ተጓዝን። ጥቂት ደቂቃዎች ዕለፉ፡፡
«እኔ የምልሽ» ብዩ ጀመርኩና «እስኪ ይኸው አሁን ብቻችንን ነን እውነቱን ንገሪኝ ታፈቅሪኛለሽ?» ብዬ ጠየቅኋት። የምትመልስልኝን ለመስማት ጆሮዩን ቀሰርኩ፡፡ አንደበቷን ከባድ ኃፍረት እየተጫነው «የትልቅ ሰው ዘር
ናቸው:: ዞር ብለውም አያዩኝ፣ እኔም የሰው አገር ሰው ነኝ እያልኩ ነው እንጂ
ማፍቀሩንማ መጀመሪያውኑ...» ብላ በዚያ ስስ ጨለማ ውስጥ የፊቴን ሁኔታ
ማየት ትችል ይመስል ትኩር ብላ አየችኝ።
«እንዲሀ አድርገናል፣ እንዲህ ሠርተናል ብለሽ አትናገሪም? ከዚህ ቀደም
በተናገርኩሽና በተቆጣሁሽ ምክንያት አልተቀየምሽም?» ብዬ ሁለቱንም ትከሻዋን ያዝኩ፡፡
«የምን መቀየም? ኸረ እኔ ከየቴ! እንዲያውም ደስ ደስ ነበር የሚለኝ።
እኔ ምክንያታቸውን እንጃ፡ አንድ ሰሞን እናትዎ ፊት ሲነሡኝ ነገሩሩን ሁሉ
ውጩ ዝም ያልኩት እርስዎን በማየት ነበር» ብላ በትኩስ ደም ጢም ያሉ
ጣቶቿን ባንገቴ ዙሪያ ዘረጋቻቸው:: ደቂቃዎቹ ጭልፊት እንዳየች ጫጩት
በነበር ጢሻ ውስጥ ለመሰግሰግ ሸመጠጡ፡፡
«እሜቴና ጌቶች ከተኙ ቆይተዋል» ብሎ በሹሉክታ ገብቶ ምድር ቤት ውስጥ የተኛው ዘበኛ እንዳይሰማን ኮሽታ ሳናሰማ ወደ ውሃው ቧንቧ ተመለስንና ተላያየን፡፡
የውጪውን ደረጃ በቀስታ ከዘለቅሁ በኋላ መብራቱን አብርቼ ወደ ክፍሌ ገባሁ። ወዲያው ልብሴን አወላልቄ አልጋዬ ላይ ተሸመለልኩ፡፡ አምስት ደቂቃ
በማይሞላ ጊዜ ውስጥ የመኝታ ቤቴ በር በዝግታ ተከፈተ፡፡ እሷው መሆኗን
በአረማመዷ ለይቻት ነበር፡፡ ያመጣችውን ውሃ አልጋዩ ሥር ከትራስጌ በኩል
ስታስቀምጥ «ገጭ» የሚል አጭር ወፍራም ድምፅ ሁለት ጊዜ ሰማሁ። በውሃ የረጠቡ እጆቿን በቀሚሷ እያደራረቀች በሩን ቀስ ብላ ከወደ ውስጥ ዘጋችው፡፡ብርድ ልብሱን ከወደ ትከሻዩ በኩል ገልጣ እጅዋን ወደ ውስጥ አሾለከች።ደረቴን አንገቴን ግንባሬንና ጉንጩን ደባበሰችኝ፡፡ እጅዋ ከግንባሬ ላይ እንደተለጠፈ ከተዘጋው የመኝታ ቤቴ መዝጊያ ውጪ ትንሽ ራቅ ብሎ የሚከፈት
በር ሲንሲያጠጥ በመስማቴ ሰውነቴ በጥርጣሬ ተንዘፈዘፈ፡፡ ልቤ በድንጋጤ
የተሰነጣጠቀች መሰለኝ፡፡
የሰው ኮቴ ተሰማ፡፡ ቁልቁል ወደ አልጋው ሥር ለመስረግ ፈለግሁ። የማይሆን አይሆንምና አልቻልኩም፡፡ የኮቴው ድምፅ እየቀረበና እየጎላ መጣ ቀረበ መጣ ቀረበ በሁኔታው ቁጥጥር ሥር በመዋሌ ፈጣን ውሳኔ ለመስጠት አዳገተኝ፡፡ የወዲያነሽ እጅዋን በፍጥነት ከግንባሬ ላይ አነሳችው::ፊቴን ገለጥ አድርጌ ሳይ ከመዝጊያው በስተጀርባ ተለጥፋለች፡፡
በሩ ከወደ ውጪ ተንኳኩቶ መጨበጫው ተነቃነቀ እና ወደ ውስጥ ተገፋ። የወዲያነሽ ከበሩ ላይ ተለጥፋ አብራ እየተገፋች የኋሊት ሄደች፡፡
ረዢም የውስጥ ልብስና ወፍራም ጋቢ ደርባ ራሷን ከፈት ባለው መዝጊያ
በኩል ወደ ውስጥ በማስገባት «ተኝተሃል እንዴ? ምነው ድምዕህ ጠፋ? ደኅና
አይደለህም እንዴ?» ያለችኝ እናቴ ነበረች። ጉድ ፈላብኝ!!
ድንጋጤ ባፈናት ደቃቃ ድምፅ ምላሴ አፌ ውስጥ እየተርበተበተች
«ደኅህ ነኝ፡ ምንም አልሆንኩም። ገና በጊዜ እኮ ነው የተኛሁት። ሂጂ ግቢ ብርድ አይምታሽ» አልኳት የሞት ሞቴን።
የወዲያነሽን ካጋጠማት የጉድ ፍላት ሥቃይና የድንጋጤ ረግረግ ውስጥ
ባስቸኳይ ለማውጣት ስል እናቴ እዚያው እንደቆመች ተሸፋፈንኩ፡፡ ሰውነቴ
ተንቀጠቀጠ። እናቴ ፊት እንደነሡት ቀላዋጭ በሩን ዘግታው ተመለሰች።
የወዲያነሽ በድንጋጤ ድርቅ ብላ ብቻዋን እንደ ቀረች ያጥር ዕንጨት ቆማለች። እጆቿ ደረቷ ላይ ተለጥፈዋል፡፡ እናቴ የመኝታ ክፍሏን በር ስትዘጋና
ትልቅ እፎይታና ግልግል! የወዲያነሽ ከወጥመድ እንዳመለጠች እይጥ በሩን ከፍታ እግሬ አውጭኝ አለች። በላዩ ላይ የወረደው የድንጋጤ ዶፍና ውርጃብኝ ወዲያው ጎደለ። በምትኩም ትዝታ እና ሰመመን እንደገና ደግሞ ትኩስ የፍቅር ሐሳብ አእምሮዬ ውስጥ “ዳንኪራና ሆታ ጀመረ::የወዲያነሽ ፈገግታ ለዛና ግልፅነት ሲነካካኝ ታወቀኝ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
...አባቴ የታላቅ ወንድሙን ጭምትነትና ልበኛነት እያስታወሰ በሚያወራበት ጊዜ ሁሉ ትዝታው በሐሳብ ፈረስ አፈናጣው ወደ አለፉት ዓመታት የኋሊት ትሰግርና ትካዜ መቀመቅ ውስጥ አገርግራ ትጥለዋለች:: መጋቢት አቦን በያመቱ እንደሚዘከርና በታላቅ መንፈሳዊ እምነት
እንደሚያምናቸው ሲያብራራ ፊቱ በኅዘን ተኮፋትሮ ዐይኖቹ በቁጣ ይጎለጎላሉ።
«ወንድሜን የገደለው የገዛ አራሹ ነው። ያውም የዋንጫውን ልቅላቂ ጠጥቶ የገበታውን ፍርፋሪ በልቶ ያደገ፡፡ የወንድሜን ገዳይ ለማስያዝና ከሕግ ፊት
አቅርቤ ለማስቀጣት በተጉላላሁ ጊዜ የደረሰብኝን ከባድ ስቃይ እስከ ዕለተ
ሞቴም አልረሳው:: ታዲያ ስፈልግና ሳስፈልግ ኖሬ ወሎ ውስጥ ከደሴ የትናየት ተንታ ከምትባል ትንሽ ከተማ ውስጥ መኖሩ በጭምጭምታ ታወቀ። ስገሠግሥ ሄድኩ፡፡ እዚያች ከተማ የገባሁት መጋቢት አራት ነበር። በማግሥቱ አሮጌ ሽማዩን ተከናንቤ ስፈልግና ሳስፈልግ ዋልኩ፡፡ መሸታ ቤቶቹ በቁጥር ናቸው።የሰው ደም አይለቅ አይደል! አንዷ ኮማሪት ቤት ተወዝፎ አምቡላውን ሲግፍ አገኘሁት፡፡ ወዲያው በነጭ ለባሽ አስያዝኩና እያካለብኩ ደሴ አስመጣሁት፡፡ገድሎ ዱር መግባቱ ቀድሞውኑ ተመስክሮና ተረጋግጦ አልቆ ስለ ነበር የኋላ ኋላ በስቅላት ተቀጣ፡፡
ልክ ባመቱ ደግሞ የአቦ ዕለት የአጥቢያ ዳኛ ሆኜ ተሾምኩ፡፡ ከአንድ ዓመት በኋላ ደግሞ ልክ የአቦ ዕለት ተካበች፣ ሙሉነህን ተገላገለች። ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሁልጊዜ እንደ ተራዱኝ ነው:: ከዚያ ወዲህ እንደ አቅሜ ጠበል ጠዲቃቸውን አስታጉዬ አላውቅም። አሁንም ቢሆን ሁልጊዜ ከጐኔ እንደ ቆሙ ናቸው፡፡ በጠበላቸውና በቃል ኪዳናቸው ነው ነፍሴ ቆማ የምትሔደው፡፡ እንደ
ሐኪሞቹ በሩን መቀባጠርማ ይኸነዬ እጓሯቸው ነበርኩ፡፡ አሁንም በሆነ
ባልሆነውና በትልቅ በትንሹ በተበሳጨሁ ቁጥር የደም ብዛቴን የሚያስታግሣልኝ
እሳቸው ናቸው። በሳቸው ጠበል ተነክሬ ከእምነታቸው ስቀምስ ዐይኔ ሁሉ
ያበራል» በማለት ያስረዳል።
በያመቱ መጋቢት አምስት ቀን በቤታችን ውስጥ ቅልጥ ያለ ድግስ ይደገሳል፡፡ የሚጠመቀው ጠላ የሚጣለው ጠጅ የሚሠራው ወጥና የሚጋገረው
እንጀራ መጠንና ብዛቱ ምን ያህል እንደሆነ የሚያውቁት እናቴና በየዓመቱ
ለዚሁ ጉዳይ የሚመጡት ሠራተኛ ሴቶች ብቻ ናቸው።
በግቢው ውስጥ ባለው ሰፊ ገላጣ ቦታ ላይ ባንድ ጊዜ ከሁለት መቶ ሰዎች በላይ ለመያዝ የሚችል ድንኳን ይጣላል፡፡ አባቴን ፍርድ ቤቱ የሚያውቀውና ዝናውን የሰማ ዘመድ
፡
፡
#ክፍል_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
...በአቅራቢያችን ያለችው ኮክ ለጋ ቅርንጫፎች ደፋ ቀና እያሉ እርስ በእርሳቸው እየተሳሳሙ ይበተናሉ፡፡ ጉንጯ ላይ ሳም ሳደርጋት የፍቅር ደማቅ ችቦ ተሀኮሰ አፌን ወደጎን አንሸራትቼ የከንፈሮቼን ነዲድ ከከንፎሮቿ አርኪ ገለት ጋር በማጋጠም ምጣድና አክንባሉ ሆንን፡፡ በሕሊናችንም ውስጥ ያ የፍቅር ችቦ ፏ ብሎ ሲቀጣጠል ታየኝ።
የወጣትነት ጣዕም፣ የፍቅር ማራኪ ለዛ፣ አንድ የመሆን ፍላጎት በዝግታ ወደ ውስጣችን ሠረፀ፡፡ ሰማይ እንደ አክንባሎ በላያችን ላይ ተደፍታ ቁልቁል ታስተውለናለች። ምን ግዳችን! የሚንቦገቦጉት ክዋክብት በጨለማው ከርስ ውስጥ የሚገኘውን ነገር ሁሉ ብርሃናዊ ውበት ሊዘሩበት ይታገላሉ። እንደ ገና ለስለስ ብሎ ከሚነፍሰው ነፋስ በተገኘው የቅጠላ ቅጠሎች ውዝዋዜ ላይ የከዋክብት ኅብራዊ ቀዝቃዛ ብርሃን ሲያርፍበት በወርቃማ ቀለም የተለበጠ ዕፅኖታዊ ሥዕል ታየ
እኔ በእርሷ የሕይወት ሰበካ፣ እሷም በእኔ የሕይወት መስክ እየተኩነሰነስን ወደማይታይና ወደማይዳስስ የሰመመን ዓለም ተጓዝን። ጥቂት ደቂቃዎች ዕለፉ፡፡
«እኔ የምልሽ» ብዩ ጀመርኩና «እስኪ ይኸው አሁን ብቻችንን ነን እውነቱን ንገሪኝ ታፈቅሪኛለሽ?» ብዬ ጠየቅኋት። የምትመልስልኝን ለመስማት ጆሮዩን ቀሰርኩ፡፡ አንደበቷን ከባድ ኃፍረት እየተጫነው «የትልቅ ሰው ዘር
ናቸው:: ዞር ብለውም አያዩኝ፣ እኔም የሰው አገር ሰው ነኝ እያልኩ ነው እንጂ
ማፍቀሩንማ መጀመሪያውኑ...» ብላ በዚያ ስስ ጨለማ ውስጥ የፊቴን ሁኔታ
ማየት ትችል ይመስል ትኩር ብላ አየችኝ።
«እንዲሀ አድርገናል፣ እንዲህ ሠርተናል ብለሽ አትናገሪም? ከዚህ ቀደም
በተናገርኩሽና በተቆጣሁሽ ምክንያት አልተቀየምሽም?» ብዬ ሁለቱንም ትከሻዋን ያዝኩ፡፡
«የምን መቀየም? ኸረ እኔ ከየቴ! እንዲያውም ደስ ደስ ነበር የሚለኝ።
እኔ ምክንያታቸውን እንጃ፡ አንድ ሰሞን እናትዎ ፊት ሲነሡኝ ነገሩሩን ሁሉ
ውጩ ዝም ያልኩት እርስዎን በማየት ነበር» ብላ በትኩስ ደም ጢም ያሉ
ጣቶቿን ባንገቴ ዙሪያ ዘረጋቻቸው:: ደቂቃዎቹ ጭልፊት እንዳየች ጫጩት
በነበር ጢሻ ውስጥ ለመሰግሰግ ሸመጠጡ፡፡
«እሜቴና ጌቶች ከተኙ ቆይተዋል» ብሎ በሹሉክታ ገብቶ ምድር ቤት ውስጥ የተኛው ዘበኛ እንዳይሰማን ኮሽታ ሳናሰማ ወደ ውሃው ቧንቧ ተመለስንና ተላያየን፡፡
የውጪውን ደረጃ በቀስታ ከዘለቅሁ በኋላ መብራቱን አብርቼ ወደ ክፍሌ ገባሁ። ወዲያው ልብሴን አወላልቄ አልጋዬ ላይ ተሸመለልኩ፡፡ አምስት ደቂቃ
በማይሞላ ጊዜ ውስጥ የመኝታ ቤቴ በር በዝግታ ተከፈተ፡፡ እሷው መሆኗን
በአረማመዷ ለይቻት ነበር፡፡ ያመጣችውን ውሃ አልጋዩ ሥር ከትራስጌ በኩል
ስታስቀምጥ «ገጭ» የሚል አጭር ወፍራም ድምፅ ሁለት ጊዜ ሰማሁ። በውሃ የረጠቡ እጆቿን በቀሚሷ እያደራረቀች በሩን ቀስ ብላ ከወደ ውስጥ ዘጋችው፡፡ብርድ ልብሱን ከወደ ትከሻዩ በኩል ገልጣ እጅዋን ወደ ውስጥ አሾለከች።ደረቴን አንገቴን ግንባሬንና ጉንጩን ደባበሰችኝ፡፡ እጅዋ ከግንባሬ ላይ እንደተለጠፈ ከተዘጋው የመኝታ ቤቴ መዝጊያ ውጪ ትንሽ ራቅ ብሎ የሚከፈት
በር ሲንሲያጠጥ በመስማቴ ሰውነቴ በጥርጣሬ ተንዘፈዘፈ፡፡ ልቤ በድንጋጤ
የተሰነጣጠቀች መሰለኝ፡፡
የሰው ኮቴ ተሰማ፡፡ ቁልቁል ወደ አልጋው ሥር ለመስረግ ፈለግሁ። የማይሆን አይሆንምና አልቻልኩም፡፡ የኮቴው ድምፅ እየቀረበና እየጎላ መጣ ቀረበ መጣ ቀረበ በሁኔታው ቁጥጥር ሥር በመዋሌ ፈጣን ውሳኔ ለመስጠት አዳገተኝ፡፡ የወዲያነሽ እጅዋን በፍጥነት ከግንባሬ ላይ አነሳችው::ፊቴን ገለጥ አድርጌ ሳይ ከመዝጊያው በስተጀርባ ተለጥፋለች፡፡
በሩ ከወደ ውጪ ተንኳኩቶ መጨበጫው ተነቃነቀ እና ወደ ውስጥ ተገፋ። የወዲያነሽ ከበሩ ላይ ተለጥፋ አብራ እየተገፋች የኋሊት ሄደች፡፡
ረዢም የውስጥ ልብስና ወፍራም ጋቢ ደርባ ራሷን ከፈት ባለው መዝጊያ
በኩል ወደ ውስጥ በማስገባት «ተኝተሃል እንዴ? ምነው ድምዕህ ጠፋ? ደኅና
አይደለህም እንዴ?» ያለችኝ እናቴ ነበረች። ጉድ ፈላብኝ!!
ድንጋጤ ባፈናት ደቃቃ ድምፅ ምላሴ አፌ ውስጥ እየተርበተበተች
«ደኅህ ነኝ፡ ምንም አልሆንኩም። ገና በጊዜ እኮ ነው የተኛሁት። ሂጂ ግቢ ብርድ አይምታሽ» አልኳት የሞት ሞቴን።
የወዲያነሽን ካጋጠማት የጉድ ፍላት ሥቃይና የድንጋጤ ረግረግ ውስጥ
ባስቸኳይ ለማውጣት ስል እናቴ እዚያው እንደቆመች ተሸፋፈንኩ፡፡ ሰውነቴ
ተንቀጠቀጠ። እናቴ ፊት እንደነሡት ቀላዋጭ በሩን ዘግታው ተመለሰች።
የወዲያነሽ በድንጋጤ ድርቅ ብላ ብቻዋን እንደ ቀረች ያጥር ዕንጨት ቆማለች። እጆቿ ደረቷ ላይ ተለጥፈዋል፡፡ እናቴ የመኝታ ክፍሏን በር ስትዘጋና
ትልቅ እፎይታና ግልግል! የወዲያነሽ ከወጥመድ እንዳመለጠች እይጥ በሩን ከፍታ እግሬ አውጭኝ አለች። በላዩ ላይ የወረደው የድንጋጤ ዶፍና ውርጃብኝ ወዲያው ጎደለ። በምትኩም ትዝታ እና ሰመመን እንደገና ደግሞ ትኩስ የፍቅር ሐሳብ አእምሮዬ ውስጥ “ዳንኪራና ሆታ ጀመረ::የወዲያነሽ ፈገግታ ለዛና ግልፅነት ሲነካካኝ ታወቀኝ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
...አባቴ የታላቅ ወንድሙን ጭምትነትና ልበኛነት እያስታወሰ በሚያወራበት ጊዜ ሁሉ ትዝታው በሐሳብ ፈረስ አፈናጣው ወደ አለፉት ዓመታት የኋሊት ትሰግርና ትካዜ መቀመቅ ውስጥ አገርግራ ትጥለዋለች:: መጋቢት አቦን በያመቱ እንደሚዘከርና በታላቅ መንፈሳዊ እምነት
እንደሚያምናቸው ሲያብራራ ፊቱ በኅዘን ተኮፋትሮ ዐይኖቹ በቁጣ ይጎለጎላሉ።
«ወንድሜን የገደለው የገዛ አራሹ ነው። ያውም የዋንጫውን ልቅላቂ ጠጥቶ የገበታውን ፍርፋሪ በልቶ ያደገ፡፡ የወንድሜን ገዳይ ለማስያዝና ከሕግ ፊት
አቅርቤ ለማስቀጣት በተጉላላሁ ጊዜ የደረሰብኝን ከባድ ስቃይ እስከ ዕለተ
ሞቴም አልረሳው:: ታዲያ ስፈልግና ሳስፈልግ ኖሬ ወሎ ውስጥ ከደሴ የትናየት ተንታ ከምትባል ትንሽ ከተማ ውስጥ መኖሩ በጭምጭምታ ታወቀ። ስገሠግሥ ሄድኩ፡፡ እዚያች ከተማ የገባሁት መጋቢት አራት ነበር። በማግሥቱ አሮጌ ሽማዩን ተከናንቤ ስፈልግና ሳስፈልግ ዋልኩ፡፡ መሸታ ቤቶቹ በቁጥር ናቸው።የሰው ደም አይለቅ አይደል! አንዷ ኮማሪት ቤት ተወዝፎ አምቡላውን ሲግፍ አገኘሁት፡፡ ወዲያው በነጭ ለባሽ አስያዝኩና እያካለብኩ ደሴ አስመጣሁት፡፡ገድሎ ዱር መግባቱ ቀድሞውኑ ተመስክሮና ተረጋግጦ አልቆ ስለ ነበር የኋላ ኋላ በስቅላት ተቀጣ፡፡
ልክ ባመቱ ደግሞ የአቦ ዕለት የአጥቢያ ዳኛ ሆኜ ተሾምኩ፡፡ ከአንድ ዓመት በኋላ ደግሞ ልክ የአቦ ዕለት ተካበች፣ ሙሉነህን ተገላገለች። ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሁልጊዜ እንደ ተራዱኝ ነው:: ከዚያ ወዲህ እንደ አቅሜ ጠበል ጠዲቃቸውን አስታጉዬ አላውቅም። አሁንም ቢሆን ሁልጊዜ ከጐኔ እንደ ቆሙ ናቸው፡፡ በጠበላቸውና በቃል ኪዳናቸው ነው ነፍሴ ቆማ የምትሔደው፡፡ እንደ
ሐኪሞቹ በሩን መቀባጠርማ ይኸነዬ እጓሯቸው ነበርኩ፡፡ አሁንም በሆነ
ባልሆነውና በትልቅ በትንሹ በተበሳጨሁ ቁጥር የደም ብዛቴን የሚያስታግሣልኝ
እሳቸው ናቸው። በሳቸው ጠበል ተነክሬ ከእምነታቸው ስቀምስ ዐይኔ ሁሉ
ያበራል» በማለት ያስረዳል።
በያመቱ መጋቢት አምስት ቀን በቤታችን ውስጥ ቅልጥ ያለ ድግስ ይደገሳል፡፡ የሚጠመቀው ጠላ የሚጣለው ጠጅ የሚሠራው ወጥና የሚጋገረው
እንጀራ መጠንና ብዛቱ ምን ያህል እንደሆነ የሚያውቁት እናቴና በየዓመቱ
ለዚሁ ጉዳይ የሚመጡት ሠራተኛ ሴቶች ብቻ ናቸው።
በግቢው ውስጥ ባለው ሰፊ ገላጣ ቦታ ላይ ባንድ ጊዜ ከሁለት መቶ ሰዎች በላይ ለመያዝ የሚችል ድንኳን ይጣላል፡፡ አባቴን ፍርድ ቤቱ የሚያውቀውና ዝናውን የሰማ ዘመድ
👍3
ይሁን እየተግተለተለ ይመጣል፡፡
ከአገር ቤት ካመጡት ሰዎች መካከል አንዳንዶቹ ሦስትና አራት ቀን
አድሪውና ሰንበትበት ብለው አተላ አፋሰው ይሔዳሉ:: ከዋዜማው ጀምሮ
ከደኅነኛው ይልቅ ሰካራሙ ስለሚበዛ ምድረ ግቢው ድብልቅልቁ ይወጣል ፡ የዕለቱ ዕለት ማታ የከተማው ሰው ጥርግ ብሎ ሲሔድ የገጠሮቹ ምድር ቤትና ድንኳን ውስጥ ሲያድሩ ቀሪዎቹ ደግሞ በያታክልቱ ስር ይለሽልሻሉ ጠምብዞ የትም የሚወድቀው ደግሞ ብዙ ነው።
የዓመቱ አቦ አሁንም ጊዜውን ቆጥሮ ደረሰ። ማንኛውም ነገር በቀድሞው
ሁኔታ ተዘጋጀ፡፡ ዕድምተኛውና ቤተኛ ነኝ ባዩ ሁሉ ከያለበት ተሰበሰበ፡፡
የወዲያነሽ በልኳ ያሰፋቸውን የሚያምር ቀሚስ ለብሳና እኅቴ ላንድ ቀን
ያዋስቻትን ሹራብ ደርባ እርጀት ያለ ውራጅ ጫማ አድርጋ በተጋባዦች መኻል
መለስ ቀሰስ ስትል ያዩዋት ሁሉ አይናቸውን ጣሉባት፡፡ ከአሥራ ሁለት ሰዓት በኋላ ተጋባዡና ጠባል ቀማሹ እየቀለለ በመሔዱ ቀሪዎቹና ቤተኛው ሁሉ በድንኳኑ ውስጥ በተንተን ብሎ እርስ በእርሱ መገባበዝ ቀጠለ:: ቀስ በቀስ
አብዛኛዎቸ ሞቅ እላቸው::
እባቴ በበኩላ የፍርድ ቤቶችና በየሙግቱ ምክንያት የሚያውቃቸውን ብዙ ሰዎች ጠርቶ ስለ ነበር ብሉልኝ ጠጡልኝ እያለ ሲጋብዝና ሲሯሯጥ በመዋሉ፣
እናቴም በፊናዋ የግል እንግዶችዋንና እንዲሁም ሌላዉን ሁሉ ወዲያ ወዲህ ስትባዝን በመዋሏ የማታ ማታ ሁለቱን በድካም ዝለው ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ ተኙ፡፡ የውብነሽም ከግማሽ ሰዓት በኋላ
ተከተለች::
ቀደም ሲል ከሶስት ወራት በፊት እናቴ ለወጂያነሽ ታዛዥነትና መልካም ጠባይ ተደስታ ለበዙ ጊዜ ምድር ቤት ውስጥ ተገትሮ የኖረ አንድ አሮጌ የብረት አልጋ ሰጥታት ነበር። እኔም ይህንን ስጦታ አስታክኬ አሮጌ ፍራሼን ጨመርኩላት፡፡
የአቦ ዕለት ማታ ግን ከገጠር የመጡ ጭሰኛ ሽማግሌ በየወዲያነሽ አልጋ
ላይ እንዲተኙ ተደረገ፡፡ አባቴ ስለ እርሳቸው ሲናገር «ታማኝ ሰው ናቸው፡
ምርት ሲሠፍሩ እፍኝ የሰው ገንዘብ አይፈልጉም፡፡ ቀኝ እጅ ናቸው» ይላል፡፡
የወዲያነሽ በድካም የዛለ ሰውነቷን የምታሳርፍበት ምቹ ጥግ አጣች።
የእኔን ልዩ እርዳታ ለማግኘት ዐይኖቿ በዐይኔ ዙሪያ ተንከራተቱ። አፍ አውጥታ
ለመናገር ኃፍረት ስለ ተጫናት ግድግዳውን ተደግፋ መቆም አበዛች።
በእንግዳ መቀበያው ክፍልና በአካባቢው ሰው አለመኖሩ እንደአረጋገጥኩ በቅድሚያ የመኝታ ቤቴን መብራት አጠፋሁ እና ዕቃ ቤቱ በር አጠገብ አንገቷን ሰበር አድርጋ የቆመችውን የወዲያነሽ ነይ አሁን ለጊዜው እዚያ ተኚ» ብዬ በክንዷ ስቢያት ገባሁ፡፡ በሩን በሚገባ ከዘጋሁት በኋላ መብራቱን አበራሁት።
«አይዞሽ አትፍሪ! እዚህ እኔ አልጋ ላይ ወጥተሽ ተኚ፡ ስንገባ ማንም አላየ» ብዬ እየተርበተበትኩ በሩን ዘግቼባት ውልቅ አልኩ፡፡
💫ይቀጥላል💫
ከአገር ቤት ካመጡት ሰዎች መካከል አንዳንዶቹ ሦስትና አራት ቀን
አድሪውና ሰንበትበት ብለው አተላ አፋሰው ይሔዳሉ:: ከዋዜማው ጀምሮ
ከደኅነኛው ይልቅ ሰካራሙ ስለሚበዛ ምድረ ግቢው ድብልቅልቁ ይወጣል ፡ የዕለቱ ዕለት ማታ የከተማው ሰው ጥርግ ብሎ ሲሔድ የገጠሮቹ ምድር ቤትና ድንኳን ውስጥ ሲያድሩ ቀሪዎቹ ደግሞ በያታክልቱ ስር ይለሽልሻሉ ጠምብዞ የትም የሚወድቀው ደግሞ ብዙ ነው።
የዓመቱ አቦ አሁንም ጊዜውን ቆጥሮ ደረሰ። ማንኛውም ነገር በቀድሞው
ሁኔታ ተዘጋጀ፡፡ ዕድምተኛውና ቤተኛ ነኝ ባዩ ሁሉ ከያለበት ተሰበሰበ፡፡
የወዲያነሽ በልኳ ያሰፋቸውን የሚያምር ቀሚስ ለብሳና እኅቴ ላንድ ቀን
ያዋስቻትን ሹራብ ደርባ እርጀት ያለ ውራጅ ጫማ አድርጋ በተጋባዦች መኻል
መለስ ቀሰስ ስትል ያዩዋት ሁሉ አይናቸውን ጣሉባት፡፡ ከአሥራ ሁለት ሰዓት በኋላ ተጋባዡና ጠባል ቀማሹ እየቀለለ በመሔዱ ቀሪዎቹና ቤተኛው ሁሉ በድንኳኑ ውስጥ በተንተን ብሎ እርስ በእርሱ መገባበዝ ቀጠለ:: ቀስ በቀስ
አብዛኛዎቸ ሞቅ እላቸው::
እባቴ በበኩላ የፍርድ ቤቶችና በየሙግቱ ምክንያት የሚያውቃቸውን ብዙ ሰዎች ጠርቶ ስለ ነበር ብሉልኝ ጠጡልኝ እያለ ሲጋብዝና ሲሯሯጥ በመዋሉ፣
እናቴም በፊናዋ የግል እንግዶችዋንና እንዲሁም ሌላዉን ሁሉ ወዲያ ወዲህ ስትባዝን በመዋሏ የማታ ማታ ሁለቱን በድካም ዝለው ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ ተኙ፡፡ የውብነሽም ከግማሽ ሰዓት በኋላ
ተከተለች::
ቀደም ሲል ከሶስት ወራት በፊት እናቴ ለወጂያነሽ ታዛዥነትና መልካም ጠባይ ተደስታ ለበዙ ጊዜ ምድር ቤት ውስጥ ተገትሮ የኖረ አንድ አሮጌ የብረት አልጋ ሰጥታት ነበር። እኔም ይህንን ስጦታ አስታክኬ አሮጌ ፍራሼን ጨመርኩላት፡፡
የአቦ ዕለት ማታ ግን ከገጠር የመጡ ጭሰኛ ሽማግሌ በየወዲያነሽ አልጋ
ላይ እንዲተኙ ተደረገ፡፡ አባቴ ስለ እርሳቸው ሲናገር «ታማኝ ሰው ናቸው፡
ምርት ሲሠፍሩ እፍኝ የሰው ገንዘብ አይፈልጉም፡፡ ቀኝ እጅ ናቸው» ይላል፡፡
የወዲያነሽ በድካም የዛለ ሰውነቷን የምታሳርፍበት ምቹ ጥግ አጣች።
የእኔን ልዩ እርዳታ ለማግኘት ዐይኖቿ በዐይኔ ዙሪያ ተንከራተቱ። አፍ አውጥታ
ለመናገር ኃፍረት ስለ ተጫናት ግድግዳውን ተደግፋ መቆም አበዛች።
በእንግዳ መቀበያው ክፍልና በአካባቢው ሰው አለመኖሩ እንደአረጋገጥኩ በቅድሚያ የመኝታ ቤቴን መብራት አጠፋሁ እና ዕቃ ቤቱ በር አጠገብ አንገቷን ሰበር አድርጋ የቆመችውን የወዲያነሽ ነይ አሁን ለጊዜው እዚያ ተኚ» ብዬ በክንዷ ስቢያት ገባሁ፡፡ በሩን በሚገባ ከዘጋሁት በኋላ መብራቱን አበራሁት።
«አይዞሽ አትፍሪ! እዚህ እኔ አልጋ ላይ ወጥተሽ ተኚ፡ ስንገባ ማንም አላየ» ብዬ እየተርበተበትኩ በሩን ዘግቼባት ውልቅ አልኩ፡፡
💫ይቀጥላል💫
👍1
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ከኮቱ ውስጥም ሽጉጥ መዝዞ በአይኗ መሀል ላይ ደቀነባት።
...ሚክ ጆንሰን ፖሊሷ ላቲሻ ሆልን ልክ እንደ ቆሻሻ እየተመለከታት
“ጉድማን በቶሎ ይፈልግሃል ብለሺኝ ነበር የመጣሁት” አላት፡፡
“አዎን መርማሪ ፖሊስ ጉድማን እንደዚያ ብለሽ ነው ደውይለት ያለኝ ጌታዬ” ብላ መለሰችለት።
ላቲሻ ከጉድማን ይልቅ ጆንሰን በጣም ንዴተኛ እንደሆነ ስለምታውቅ በጣም
ተጠንቅቃ በትህትና ነበር መልስ የምትሰጠው።ሁሉምዐየዲፓርትመንቱ ሰራተኞች ከሚክ ጆንሰን ጋር ፊት ለፊት መጋፈጥ እንደሚያዋርድ ያውቃሉ። በተለይ ደግሞ የሚጋፈጠው ሰው አይሪሽ ካቶሊክ ነጭ እና ወንድ ከሆነ ጉዱ ነው የሚፈላው፡፡
“እና የታለ እሱ?” ብሎ ጆንሰን ጥርሱን ነክሶ ጠየቃት፡፡
“አላውቅም ጌታዬ!”
“አታውቂም?!” ብሎ ጆንሰን በሹፈት መልክ ድምፁን ቀንሶ ጠየቃት::ክፍሉ ውስጥ ከሚገኘው ሶፋ ወንበር ላይም ሰምጦ ከተቀመጠ በኋላ አይኑን
በመጨፈን ንዴቱን ተቆጣጠረ። ለእሷ አስቦ ሳይሆን ሀይሉን መቆጠብ
ስላለበት ነው ንዴቱን ያላሳያት። አሁን ነገሮች በጣም አደገኛ ሆነዋል።
ስለዚህ አሁን ማወቅ ያለበት ጉድማን የት እንደሚገኝ ብቻ ነው።
ሁለቱ መርማሪ ፖሊሶች እየተወሻሹ እስከ አሁን ድረስ ዘልቀዋል። ዛሬ ላይ ደግሞ ጆንሰን የሽጉጥ ድምፅ አፋኝ የሚሸጡ ሰዎችን ሲያፈላልግ እንዳልዋለ ሁሉ ጉድማንም የመተግበሪያ አፕሊኬሽን ፈቃዱ የማን እንደሆነ ሲመረምር እንደዋለ ያውቃል። ጆንሰን የካርተር በርክሌን ባንክ ወደ ሆነው በርክሌይ ሀሞንድ ሩድ ባንክ ሄዶ ለምርመራ የሚፈልገውን ፋይል ኮፒ ሲያስደርግ በነበረበት ጊዜ ነበር በአስቸኳይ እንደሚፈለግ ይህቺ ደነዝ ሴት
ደውላ የነገረችው፡፡
ዛሬ በርክሌይ ቢሮ ውስጥ ሆኖ ነበር ጉድማን እየዋሸው ሁለቱንም ባሳወራቸው የማይገባው ዓለም ውስጥ አብሮት እንደሚሰራ የገባው። እርግጥ
ነው ገና ይሄንን ጉዳይ አብረው ምርመራ ማድረግ ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ
ደመ ነፍሱ ጉድማንን እንደማያምነው ሲነግረው ነበር።
“መርማሪ ፖሊስ ጉድማን እዚህ አንተን እየጠበቀ ባለበት ጊዜ ላይ ነበር
ስልክ የተደወለለት::” አለች እና ላቲሻ በመቀጠልም “የደወለለትን ሰው ማንነት ባላውቅም ስልኩን ካወራ በኋላ ልክ ከሲኦል ተመንጥቆ እንደወጣ የሌሊት ወፍ በፍጥነት ነበር ከዚህ ቢሮ የወጣው። ፊቱ ላይ የሚታየው ነገርን ሳልጨምር ማለት ነው”
የጆንስን አዕምሮ የተለያዩ ነገሮችን እያሰበ ሆዱን ፍርሃት ፍርሀት አለው።
ላቲሻን ከእሱ እና ጉድማን የጋራ ቢሮ አስወጣት እና በሩን ዘግቶ የጉድማን ወንበር ላይ ቁጭ አለ።
አሁን ነገሩ እየከረረ ነው ፤ ነገር ግን ተስፋ መቁረጥ አይኖርበትም፡፡
አስብ!”
የጉድማን ዴስክ ሁሌም ጥርት ያለ እና የተደራጀ ነው። የዶክተር ሮበርትስ አድራሻ ከጀርባው የተፃፈበት ኤንቨሎፕ እና የጉድማን ስልክ ዴስኩ ላይ ይገኛሉ። ይሄ ደግሞ ጉድማን በጣም በከፍተኛ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ በመሆኑ የተነሳ ነው እንጂ ጉድማን ስልኩን ረስቶ መቼም እንደማይሄድ ያውቀዋል። ጆንሰን ኤንቨሎፕን አንስቶ የዊሊያምስን ደረሰኝ እና ከጀርባው የተፃፈውን የኒኪን እጅ ፅሁፍ ማስታወሻውን በጥንቃቄ ሲመለከት ቆየ።
በተለይ ደግሞ የእሱን ስም ከኤንቨሎፕ ላይ ሲያነብ ልቡን አፈነው። ጆንሰን
እዚህ ነገር ውስጥ እስከ አንገቱ ነው ያለበት! የማትረባ ሴት! አንገት ድረስ
መጥለቅ ምን ማለት እንደሆነ ሊያሳያት ነበር።
ኤንቨሎፕን ኪሱ ውስጥ ከተተ እና የጉድማንን ስልክ አንስቶ ከበፊት
ጀምሮ ሸምድዶ የያዘውን የስልኩን ኮድ ቁጥር ፃፈ እና ከፈተው።የመልዕክት ሳጥኑን እና የደወላቸውን ቁጥሮች በጣቱ ወደ ታች ሲያደርግ ቆይቶ በመጨረሻ ላይ የሚፈልገውን ነገር አገኘ።
ወደ ራሱ ስልክም ከጉድማን ስልክ ላይ ያለውን መረጃ አዘዋወረ እና የተላከ መልዕክት የሚለው ቦታ ላይ ገብቶም መረጃውን አጠፋ:: ሰዓቱን ሲመለከትም ልቡ በፍርሃት መደለቅ ጀመረች፡፡ 12:20 ይላል! ይሄ እንዴት ሊሆን ቻለ? ምናልባት ዘግይቶ ቢሆንስ?
ሽጉጡን እና ተጨማሪ የሽጉጡ ካርታዎች ቀልሃቸው ሙሉ መሆኑን አረጋግጦም በሩን ከፍቶ እየሮጠ ወጣ፡፡
አሁን ይህንን የተረገመ ምርመራ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ መጨረስ ይኖርበታል።
ኒኪ አይኗን ጨፍና ህይወቷን የሚያሳጣትን ጥይት ድምፅ እየጠበቀች
ነው። የዊሊን ሬሳ ስታይ የተሰማት ከፍተኛ ፍርሃት በንኖ ጠፋ እና በተስፋ መቁረጥ ተተካ፡፡ በተለይ ደግሞ ለማወቅ የምትፈልጋቸውን ነገሮች ሳታውቅ
መሞቷን ስታስብ ድንዛዜ ተቆጣጠራት፡፡
የምትጠብቀው የጥይት ድምፅን መስማት አልቻለችም። አይኗን
ስትገልፅም የሮድሪጌዝ አይኖች ላይ ጭካኔን እና መገረምን ተመለከተች፡፡
“ምን ያስቸኩልሻል ዶክተር ሮበርትስ፡፡ ወደ ፈጣሪሽ ከመሄድሽ በፊት ማውራት አትፈልጊም እንዴ?” አላት፡፡
“ዊሊ ባደንን አንተ ነህ የገደልከው?” ብላ በእርጋታ ጠየቀችው። እርግጥ ነው ሊገድላት ነው። ግን ከመሞቷ በፊት መልሶችን መስማት ትፈልጋላች፡፡
“ታዲያስ?” ብሎ ምስጋና የሚሰጣት ይመስል አጎነበሰ፡፡
“ለምን?
“ለምን አልገድለውም?” ብሎ ሳቀባት እና “እንዴ ያደረግኩትን ሥራ እንዳልወደድሽው እያየሁ እንዳይሆን ብቻ! የሆነ አጭበርባሪ አሳማ ነገር እኮ
ነው።”
“ለምን?”
“ተስገበገበአ!” አላት እና በመቀጠልም “አብረን በምንሰራው ቢዝነስ ውስጥ
ሜክሲኮ ውስጥ ከተስማማነው ውጪ ብዙ ገንዘብ ከእኔ ላይ መውሰድ
ጀመረ። ሜክሲኮ እያለን ጠንቃቃ ነበር፡፡ እዚህ ሎስ አንጀለስ ከመጣ በኋላ
ግን ራሱን አይነኬ አድርጎ መቁጠር ጀመረ፡፡” አላት እና ወደ ዊሊ ሬሳ ዞሮ
“ይህ ሀሳቡ ደግሞ የማይረባ እና ስህተት እንደሆነ ላሳየው ፈለግኩኝ። ማንም ሰው ከእኔ ጋር ጠላትነት ውስጥ ከገባ የትም ቢገባ ፈልጌ አገኘዋለሁ::” ካላት በኋላ በጣም በሚያስፈራ ሁኔታ አፍጥጦ ሲያያት ኒኪ ወዲያውኑ ተኩሶ የሚገድላት መስላት:: “እሺ ሌላ ጥያቄ አለሽ?” አላት፡፡
“እኔን ምንድነው ያደረግካት?”
ሮድሪጌዝም በጥያቄዋ ተገርሞ አያት እና
“እኔን እሷ እንዲደረግባት ከምትፈልጋቸው ነገሮች ውጪ ምንም ነገር አላደረኳትም” አለ እና ፈገግ ብሎም
“ሚስቴ ሰዎች እንዲጫኗት ትፈልጋለች። ዶክተር ሮበርትስ አንቺ ይሄ የሚስቴ ነገር ለምን እንዳልገባሽ አላውቅም። አሁንም ቢሆን ይሄ ነገር አይገባሽም። ምክንያቱም አኔን ከእኔ በላይ አታውቂያትም።”
“በጣም እንደምትፈራህ አውቃለሁ” አለችው እና ኒኪ በመቀጠልም
አንተ ሸሽታ ወደ እዚህ የመጣችው አንተ አስረሃት የምትኖረው ኑሮ ከአቅሟ በላይ ስለሆነባት ነው” ስትለው ፈገግታው ጨለመ::
አንቺ ስለ እሷ ስትከራከሪላት ሳይ በጣም ይገርመኛል፡፡ እንዴ! ወደዚህ
ልታስገድልሽ እንደሆነ እያወቅሽ መሆኑ ደግሞ የባሰ አስደምሞኛል።” አላት፡፡
“ምክንያቱም ስላስገደድካት ነው! የዊሊ ባድንን ግድያ አስገድደህ እንድታየው እንዳደረካት ሁሉ ማለት ነው።” አለችው፡፡
ሊዊስም ራሱን በአሉታ ነቅንቆ “ዶክተር ሮበርትስ ነገሩ እስካሁን አልገባሽም ማለት ነው? እሷ ይህንን ነገር የምታደርግልኝ እኮ በጣም
ስለምትወደኝ ነው። ላንቺ ምንም አይነት ስሜት ቢኖራትም በመጨረሻ ላይ
አኔ እኔን ለመከላከል ስትል ማንኛውንም ነገር ታደርግልኛለች። ምንም እንኳን በመካከላችን ያለውን ፍቅር ልታጠፊ ያላደረግሽው ነገር ባይኖርም
አኔ ልቧ አሁንም ከእኔ ጋር ነው።”
“ውሸት!” ብላ ኒኪ ከመለሰችለት በኋላ ግን ደውላ ወደዚህ እንዳስመጣቻትና እንዲሁም ደግሞ በዊሊ ባደን ግድያ ላይ ስለነበራት ድርሻ ምን ይሆን? ብላ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ከኮቱ ውስጥም ሽጉጥ መዝዞ በአይኗ መሀል ላይ ደቀነባት።
...ሚክ ጆንሰን ፖሊሷ ላቲሻ ሆልን ልክ እንደ ቆሻሻ እየተመለከታት
“ጉድማን በቶሎ ይፈልግሃል ብለሺኝ ነበር የመጣሁት” አላት፡፡
“አዎን መርማሪ ፖሊስ ጉድማን እንደዚያ ብለሽ ነው ደውይለት ያለኝ ጌታዬ” ብላ መለሰችለት።
ላቲሻ ከጉድማን ይልቅ ጆንሰን በጣም ንዴተኛ እንደሆነ ስለምታውቅ በጣም
ተጠንቅቃ በትህትና ነበር መልስ የምትሰጠው።ሁሉምዐየዲፓርትመንቱ ሰራተኞች ከሚክ ጆንሰን ጋር ፊት ለፊት መጋፈጥ እንደሚያዋርድ ያውቃሉ። በተለይ ደግሞ የሚጋፈጠው ሰው አይሪሽ ካቶሊክ ነጭ እና ወንድ ከሆነ ጉዱ ነው የሚፈላው፡፡
“እና የታለ እሱ?” ብሎ ጆንሰን ጥርሱን ነክሶ ጠየቃት፡፡
“አላውቅም ጌታዬ!”
“አታውቂም?!” ብሎ ጆንሰን በሹፈት መልክ ድምፁን ቀንሶ ጠየቃት::ክፍሉ ውስጥ ከሚገኘው ሶፋ ወንበር ላይም ሰምጦ ከተቀመጠ በኋላ አይኑን
በመጨፈን ንዴቱን ተቆጣጠረ። ለእሷ አስቦ ሳይሆን ሀይሉን መቆጠብ
ስላለበት ነው ንዴቱን ያላሳያት። አሁን ነገሮች በጣም አደገኛ ሆነዋል።
ስለዚህ አሁን ማወቅ ያለበት ጉድማን የት እንደሚገኝ ብቻ ነው።
ሁለቱ መርማሪ ፖሊሶች እየተወሻሹ እስከ አሁን ድረስ ዘልቀዋል። ዛሬ ላይ ደግሞ ጆንሰን የሽጉጥ ድምፅ አፋኝ የሚሸጡ ሰዎችን ሲያፈላልግ እንዳልዋለ ሁሉ ጉድማንም የመተግበሪያ አፕሊኬሽን ፈቃዱ የማን እንደሆነ ሲመረምር እንደዋለ ያውቃል። ጆንሰን የካርተር በርክሌን ባንክ ወደ ሆነው በርክሌይ ሀሞንድ ሩድ ባንክ ሄዶ ለምርመራ የሚፈልገውን ፋይል ኮፒ ሲያስደርግ በነበረበት ጊዜ ነበር በአስቸኳይ እንደሚፈለግ ይህቺ ደነዝ ሴት
ደውላ የነገረችው፡፡
ዛሬ በርክሌይ ቢሮ ውስጥ ሆኖ ነበር ጉድማን እየዋሸው ሁለቱንም ባሳወራቸው የማይገባው ዓለም ውስጥ አብሮት እንደሚሰራ የገባው። እርግጥ
ነው ገና ይሄንን ጉዳይ አብረው ምርመራ ማድረግ ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ
ደመ ነፍሱ ጉድማንን እንደማያምነው ሲነግረው ነበር።
“መርማሪ ፖሊስ ጉድማን እዚህ አንተን እየጠበቀ ባለበት ጊዜ ላይ ነበር
ስልክ የተደወለለት::” አለች እና ላቲሻ በመቀጠልም “የደወለለትን ሰው ማንነት ባላውቅም ስልኩን ካወራ በኋላ ልክ ከሲኦል ተመንጥቆ እንደወጣ የሌሊት ወፍ በፍጥነት ነበር ከዚህ ቢሮ የወጣው። ፊቱ ላይ የሚታየው ነገርን ሳልጨምር ማለት ነው”
የጆንስን አዕምሮ የተለያዩ ነገሮችን እያሰበ ሆዱን ፍርሃት ፍርሀት አለው።
ላቲሻን ከእሱ እና ጉድማን የጋራ ቢሮ አስወጣት እና በሩን ዘግቶ የጉድማን ወንበር ላይ ቁጭ አለ።
አሁን ነገሩ እየከረረ ነው ፤ ነገር ግን ተስፋ መቁረጥ አይኖርበትም፡፡
አስብ!”
የጉድማን ዴስክ ሁሌም ጥርት ያለ እና የተደራጀ ነው። የዶክተር ሮበርትስ አድራሻ ከጀርባው የተፃፈበት ኤንቨሎፕ እና የጉድማን ስልክ ዴስኩ ላይ ይገኛሉ። ይሄ ደግሞ ጉድማን በጣም በከፍተኛ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ በመሆኑ የተነሳ ነው እንጂ ጉድማን ስልኩን ረስቶ መቼም እንደማይሄድ ያውቀዋል። ጆንሰን ኤንቨሎፕን አንስቶ የዊሊያምስን ደረሰኝ እና ከጀርባው የተፃፈውን የኒኪን እጅ ፅሁፍ ማስታወሻውን በጥንቃቄ ሲመለከት ቆየ።
በተለይ ደግሞ የእሱን ስም ከኤንቨሎፕ ላይ ሲያነብ ልቡን አፈነው። ጆንሰን
እዚህ ነገር ውስጥ እስከ አንገቱ ነው ያለበት! የማትረባ ሴት! አንገት ድረስ
መጥለቅ ምን ማለት እንደሆነ ሊያሳያት ነበር።
ኤንቨሎፕን ኪሱ ውስጥ ከተተ እና የጉድማንን ስልክ አንስቶ ከበፊት
ጀምሮ ሸምድዶ የያዘውን የስልኩን ኮድ ቁጥር ፃፈ እና ከፈተው።የመልዕክት ሳጥኑን እና የደወላቸውን ቁጥሮች በጣቱ ወደ ታች ሲያደርግ ቆይቶ በመጨረሻ ላይ የሚፈልገውን ነገር አገኘ።
ወደ ራሱ ስልክም ከጉድማን ስልክ ላይ ያለውን መረጃ አዘዋወረ እና የተላከ መልዕክት የሚለው ቦታ ላይ ገብቶም መረጃውን አጠፋ:: ሰዓቱን ሲመለከትም ልቡ በፍርሃት መደለቅ ጀመረች፡፡ 12:20 ይላል! ይሄ እንዴት ሊሆን ቻለ? ምናልባት ዘግይቶ ቢሆንስ?
ሽጉጡን እና ተጨማሪ የሽጉጡ ካርታዎች ቀልሃቸው ሙሉ መሆኑን አረጋግጦም በሩን ከፍቶ እየሮጠ ወጣ፡፡
አሁን ይህንን የተረገመ ምርመራ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ መጨረስ ይኖርበታል።
ኒኪ አይኗን ጨፍና ህይወቷን የሚያሳጣትን ጥይት ድምፅ እየጠበቀች
ነው። የዊሊን ሬሳ ስታይ የተሰማት ከፍተኛ ፍርሃት በንኖ ጠፋ እና በተስፋ መቁረጥ ተተካ፡፡ በተለይ ደግሞ ለማወቅ የምትፈልጋቸውን ነገሮች ሳታውቅ
መሞቷን ስታስብ ድንዛዜ ተቆጣጠራት፡፡
የምትጠብቀው የጥይት ድምፅን መስማት አልቻለችም። አይኗን
ስትገልፅም የሮድሪጌዝ አይኖች ላይ ጭካኔን እና መገረምን ተመለከተች፡፡
“ምን ያስቸኩልሻል ዶክተር ሮበርትስ፡፡ ወደ ፈጣሪሽ ከመሄድሽ በፊት ማውራት አትፈልጊም እንዴ?” አላት፡፡
“ዊሊ ባደንን አንተ ነህ የገደልከው?” ብላ በእርጋታ ጠየቀችው። እርግጥ ነው ሊገድላት ነው። ግን ከመሞቷ በፊት መልሶችን መስማት ትፈልጋላች፡፡
“ታዲያስ?” ብሎ ምስጋና የሚሰጣት ይመስል አጎነበሰ፡፡
“ለምን?
“ለምን አልገድለውም?” ብሎ ሳቀባት እና “እንዴ ያደረግኩትን ሥራ እንዳልወደድሽው እያየሁ እንዳይሆን ብቻ! የሆነ አጭበርባሪ አሳማ ነገር እኮ
ነው።”
“ለምን?”
“ተስገበገበአ!” አላት እና በመቀጠልም “አብረን በምንሰራው ቢዝነስ ውስጥ
ሜክሲኮ ውስጥ ከተስማማነው ውጪ ብዙ ገንዘብ ከእኔ ላይ መውሰድ
ጀመረ። ሜክሲኮ እያለን ጠንቃቃ ነበር፡፡ እዚህ ሎስ አንጀለስ ከመጣ በኋላ
ግን ራሱን አይነኬ አድርጎ መቁጠር ጀመረ፡፡” አላት እና ወደ ዊሊ ሬሳ ዞሮ
“ይህ ሀሳቡ ደግሞ የማይረባ እና ስህተት እንደሆነ ላሳየው ፈለግኩኝ። ማንም ሰው ከእኔ ጋር ጠላትነት ውስጥ ከገባ የትም ቢገባ ፈልጌ አገኘዋለሁ::” ካላት በኋላ በጣም በሚያስፈራ ሁኔታ አፍጥጦ ሲያያት ኒኪ ወዲያውኑ ተኩሶ የሚገድላት መስላት:: “እሺ ሌላ ጥያቄ አለሽ?” አላት፡፡
“እኔን ምንድነው ያደረግካት?”
ሮድሪጌዝም በጥያቄዋ ተገርሞ አያት እና
“እኔን እሷ እንዲደረግባት ከምትፈልጋቸው ነገሮች ውጪ ምንም ነገር አላደረኳትም” አለ እና ፈገግ ብሎም
“ሚስቴ ሰዎች እንዲጫኗት ትፈልጋለች። ዶክተር ሮበርትስ አንቺ ይሄ የሚስቴ ነገር ለምን እንዳልገባሽ አላውቅም። አሁንም ቢሆን ይሄ ነገር አይገባሽም። ምክንያቱም አኔን ከእኔ በላይ አታውቂያትም።”
“በጣም እንደምትፈራህ አውቃለሁ” አለችው እና ኒኪ በመቀጠልም
አንተ ሸሽታ ወደ እዚህ የመጣችው አንተ አስረሃት የምትኖረው ኑሮ ከአቅሟ በላይ ስለሆነባት ነው” ስትለው ፈገግታው ጨለመ::
አንቺ ስለ እሷ ስትከራከሪላት ሳይ በጣም ይገርመኛል፡፡ እንዴ! ወደዚህ
ልታስገድልሽ እንደሆነ እያወቅሽ መሆኑ ደግሞ የባሰ አስደምሞኛል።” አላት፡፡
“ምክንያቱም ስላስገደድካት ነው! የዊሊ ባድንን ግድያ አስገድደህ እንድታየው እንዳደረካት ሁሉ ማለት ነው።” አለችው፡፡
ሊዊስም ራሱን በአሉታ ነቅንቆ “ዶክተር ሮበርትስ ነገሩ እስካሁን አልገባሽም ማለት ነው? እሷ ይህንን ነገር የምታደርግልኝ እኮ በጣም
ስለምትወደኝ ነው። ላንቺ ምንም አይነት ስሜት ቢኖራትም በመጨረሻ ላይ
አኔ እኔን ለመከላከል ስትል ማንኛውንም ነገር ታደርግልኛለች። ምንም እንኳን በመካከላችን ያለውን ፍቅር ልታጠፊ ያላደረግሽው ነገር ባይኖርም
አኔ ልቧ አሁንም ከእኔ ጋር ነው።”
“ውሸት!” ብላ ኒኪ ከመለሰችለት በኋላ ግን ደውላ ወደዚህ እንዳስመጣቻትና እንዲሁም ደግሞ በዊሊ ባደን ግድያ ላይ ስለነበራት ድርሻ ምን ይሆን? ብላ
❤1👍1
ራሷን ስትጠይቅ ስሜቷን አረጋጋች፡፡
“ከብዙ ጊዜ በፊት ነበር አንቺን ማስወገድ የነበረብኝ” ብሎ ሉዊስ ማውራቱን ቀጠለ “ባይገርምሽ ገና ከሚስቴ ጋር ከመገናኘታችሁ በፊት ነበር
ላስወግድሽ የነበረው:: አየሽ ገና በርክሌ ወደ አንቺ ቢሮ ለቴራፒ ህክምና
ሲመጣ እና ዕብደቱ ሲጀምረው ነበር ላጠፋሽ የነበረው።”
“ካርተርን ነው የምትለኝ?” አለችው ኒኪ በግርምት ተሞልታ። ካርተር
በርክሌይ ከዚህ ጋር ምን የሚያገናኘው ነገር አለው::”
ሉዊስም ፈገግ ብሎ “የእውነት አታውቂም አይደል?”
“አላውቅም” ብላ መለሰችለት፡፡
መልካም ዶክተር ሮበርትስ እንደርሱ ከሆነማ አጭር ተረት ልንገርሻ?
ነገሮችን አገጣጥመሽ እንድትደርሺባቸው እና ዘና እንድትይ አስቤ ነው
ታዲያ ይህንን ተረት የምተርክልሽ፡፡ በድሮ ጊዜ አንድ ሰውዬ ነበር። ይሄ ሰው ግን ወጣት ሳይሆን ከወጣትነት ዕድሜው በትንሹ ያለፈ ሰው ነበር::
ብሎ ሉዊስ የተዋናይ ድምፅ በሆነ መልኩ ትረካውን ቀጠለ፡፡ ድምፁ
የሆነ ደስ የሚል እና ድንዘዝ የሚያደርግ ነገር አለው። ስለዚህም ኒኪ እሱ
እንዴት አድርጎ ወጣቷን አኔን በዚህ መልኩ እንደሚጫወትባት እያሰበች
ትረካውን ማዳመጥ ቀጠለች።
“ሰውዬውን ከሜክሲኮ ሲቲ ከተማ በጥቂት ማይል ርቀት ላይ ከሚገኝ
ጫካ ውስጥ እንደሚገኝ አስቢው፡፡ ቦታው ሞቃት ነው፤ ጨለማ ጊዜ ላይ::
ጨረቃዋ ሙሉ ናት፡፡ ለወራቶች ያህል በጣም የሚያስደስተውን ለስላሳ
የወጣት ገላውን እንደዚያን ቀን አስደስቶት አያውቅም። ያን ዕለት ማታ ሰውዬውን በጣም የተለየ ምርጥ ምሽትን እንዲያሳልፍ ታደርገዋለች::”
ኒኪ ውስጧን ብርድ ብርድ
ሲላት ይታወቃታል። ሰውነቷም
መንቀጥቀጥ ጀመረ። ይህንን ሲያይ ደግሞ የሮድሪጌዝ ፊት በደስታ በራ::
ባለፈው ካርተር በርክሌይን ስታክመው የነገራትን ነገር እያስታወሰች በቀድሞ
ትውስታዋ ውስጥ ተመስጣ ትስመው ጀመር “ቦታው የተመነጠረ ነው::
ምሽት ነበር፡፡ ጭለማ ቢሆንም የጨረቃ ብርሃን ግን ነበር። በጣም ይሞቃል”
የሚለው የካርተር በርክሌይ ድምፅ ጆሮዋ ላይ ደወለባት።
“ስትመጣ አያት” ሮድሪጌዝ ትረካውን ቀጠለ “ሜዳውን እየተደናቀፈች
አቋርጣ ስልኳ ላይ ያለውን የካርታ አድራሻንም ተመለከተች፡፡ ቀይ ፀጉሯ
እሷ ስትራመድ በግራ እና በቀኝ ይወዛወዛል። ረዥም ናት። በጣም ረዥም
ቀጭን ሸንቀጥ ያለች። በእግሮቿ የተሰባበሩትን የዛፍ ቅርንጫፎችን
እየረገጠች ስትመጣ የአዳኝ አይን ውስጥ የገባች ሚዳቆ ትመስል ነበር። ምርጥ ነገር! በጣም ቆንጆ ናት። በዚያ ላይ ደግሞ ገና ለጋ ወጣት? ከእኔ
ጋር ነሽ ዶክተር ሮበርትስ?”
ኒኪ ራሷን በአዎንታ ነቀነቀችለት፡፡ አሁን ሁሉ ነገር ግልፅ ሆነላት። ነገሮቹን ገጣጥማ የሆነ ነገር ላይ ደርሳለች፡፡
“ቻርሎቴ ክላንስ! የምታወራው ስለ ቻርሎቴ ክላንሲ ነው አይደል?”
“በጣም ጎበዝ ነሽ” ብሎ ሮድሪጌዝ ገለፈጠና “ ከሁሉም ነገሯ ሰውዬው
ወደ እሷ እንዲሳብ ያደረገው የዋህነቷ ነበር:: የሆነ እሱ ጋር የሌለው ነገር
ስለነበር ይህንን ነገሯን በጣም ይወድላታል፡፡ ከረዥም ጊዜያት በፊት እሱም ወጣት ነበር፡፡ ግን እንደ እሷ አልነበረም። ሁለቱም የተለያዩ ዓለም ሰዎች ናቸው። ኮከባቸው ሊገጥም የማይገባ ነበር ግን እንዲሁ በድንገት የገጠመ ሆነ። ይሄው ወደ እሱ እየሮጠች ስትመጣ ያያታል።”
“ከዚያስ ምን ተከሰተ?” ብላ ኒኪ ጠየቀችው:: ስትጠይቀው ልክ
ታካሚዎቿን ውስጣቸው ያለውን ነገር እንዲያወጡ በምትጠይቅበት መልኩ
“ከዚያማ ሰውዬው ከመኪናው ውስጥ ወጣ እና ቀስ እያለ ለመቶ ጫማ
ያህል ወደተመነጠረው ቦታ ሄደ። እዚያ ስትደርስ ሰላም ብሎ ሊቀበላት አስቦ
ነው እንግዲህ።” አላት እና ሮድሪጌዝ
የወሲብ ስሜት ተቀስቅሶበታል። ደስ ብሎታል፡፡ ይህንን ነገር ደግሞ
በጣም ይፈልገዋል እና እዚያው ጭለማው ውስጥ እንዳለም
“ቻራ!” ብሎ ጠራት፡፡
“እዚህ ነኝ ፍቅሬ!” አላት ልክ የቻርሎቴን ድምፅ አስመስሎ፡፡ “ከዚያም የተመነጠረው ቦታ ላይ ደረሰች፡፡ ከእሱ 10 ጫማ ርቀት ላይ እያፈረች ቆመች። ወደ እሱ ልትመጣ ስትንቀሳቀስ ግን በእጁ እዚያው እንድትቆም ነገራት፡፡ እዚህ ቦታ ላይ እንደዚህ ቆማ ለዘላለም ሊያስባት እንደሚፈልግም ነገራት።
ይታይሻል አይደል?” አላት ሉዊስ ኒኪን፡፡
“አዎን ትታየኛለች” አለችው እና በመቀጠልም “ግን እኮ ገና 18 ዓመት
የሆናት ልጅ ናት፡፡ ሉዊስ ምንድነው ያደረግካት?” ብላ ጠየቀችው፡፡
እሱም በትንሹ ጎንበስ ብሎ አመስግኖ አሾፈባት እና ትንሽ ስቆም “ልክ ነሽ በድጋሚ ዶክተር ሮበርትስ። ወጣቷ ልጅ ቻርሎቴ ስትሆን ሰውዬው ደግሞ እኔ ነበርኩኝ፡፡ ደርሰሽበታል በእውነት ጎበዝ ነሽ፡፡ ያኔ ከሁለተኛዋ ሚስቴ ጋር ተጋብቼ እኖር ነበር፡፡ ይሄ የሆነው አኔን ከማግኘቴ ከጥቂት ዓመታት በፊት ነበር፡፡ የሚገርም የበጋ ወራት ከቻርሎቴ ጋር በፍቅር
አሳልፌ ነበር፡፡ ግን እንደ አለመታደል ሆኖ ቻርሎቴ መሄድ የማይገባትን
መንገድ ሄዳ ድንበሬን አለፈች፡፡
የጀመርኩትን ነገሮች ከመጨረስ በስተቀር ምንም አይነት ምርጫ አልተወችልኝም ነበር።”
ምን አደረግኳት? አዎን ቀሚሷን እንድታወልቀው ነገርኳት። ልክ እንደ
አኔ ሁሉ እሷም እኔ ጫና እንዳሳድርባት ትፈልጋለች: ትዕዛዞቼን ለመፈፀም
ሁሌም ዝግጁ እና ጉጉም ነበረች” አላት እና ሁኔታውን አስታውሶ ምራቁን
ከዋጠ በኋላ አቤት እጇን ወደ ላይ ከፍ አድርጋ ከጥጥ የተሰራው ልብሷን
ስታወልቅ አሁን ድረስ አይኔ ላይ አለ።
ፖም የሚያካክሉ የሚጣፍጡ መካከለኛ ጡቶች አላት። ልሙጥ ያለው ሆዷም ከፖንቷ በላይ ይታየኛል፡፡ ዋው! ምንኛ ተአምር ነበር መሰለሽ ዶክተር ሮበርት። ከዚያም ደንሺልኝ አልኳት። እሷ ግን በጣም ከማፈሯ የተነሳ ልትደንስልኝ አልቻለችም። ስለዚህ እንድትደንስልኝ ትንሽ እገዛ አደረኩላት፡፡ ከዚህ በፊት የሰው ልጅ በአውቶማቲክ ጠመንጃ በተከታታይ ሲመታ አይተሽ ታውቂያለሽ?” አላት እና አስፈሪ ሳቁን ስቆ “አይተሽ
የምታውቂ አይመስለኝም፤ መሬት ላይ ከመውደቃቸው በፊት ህይወታችው
ወጥቷል፡፡ ግን መሬት ላይ ከመውደቃቸው በፊት አየር ላይ የሚያደርጉት መንቀጥቀጥ፣ መዝለል፣ መንዘፍዘፍ እና እግራቸውን በተለያዩ አቅጣጫዎች በማይታመን ሁኔታ የሚያወናጭፋቸው ነገር እንዴት ደስ ይላል መሰለሽ:: ምን ያደርጋል ታዲያ መጨረሻ ላይ መሬት ሲወድቁ ይሄ ሁሉ አስደናቂ ዳንሳቸው ያበቃል።” ቀጠለናም
ካርተር በርክሌይ የእኔ ባንከር ነበር፡፡ ደስ ይለኝ ነበር። ግን በቃ በጣም ሁሉ ነገሩ የተቋጠረ ሰው ነበር። ለማንኛውም ቻርሎቴ በምታሳየው ትርዒት ትንሽ ይዝናና ብዬ ስላሰብኩኝ ነበር ያን ቀን ይሄው ወደ ቦታው ያመራሁት፡፡ እሱ ስለሆነ ያስተዋወቀን ቢያንስ ትንሽዬ
ያስፈልገዋል፡፡ ስለዚህም እሱን የሚያስደስት ነገር እንዳዘጋጀሁለት ነግሬው ነበር በእኔ መኪና ይዤው የወጣሁት፡፡ ግን ምን ያደርጋል ባየው ነገር መኪና ውስጥ ተቀምጦ በፍርሃት እና በድንጋጤ ይንቀጠቀጥ ጀመር።
ይመስለኛል ቻርሎቴ እንደዋዛ የምፈቅድለት መስሎት ነበር እዚህ
የመጣው።” አላት እና ከት ብሎ ሳቁን ለቀቀው፡፡
“ደግሞስ ለምንድነው በቻርሎቴ እንዲዝናና የምፈቅድለት? ምክንያቱም
የእኔ የሆነ ነገር ሁሉ የእኔ ብቻ ነው”
ኒኪም የነገራትን ነገር ለሰኮንዶች ያህል እያሰበች ዊሊያምስ ከመሞቱ
በፊት የነገራትን ነገር አስታውሳም
“ስለዚህ ካርተር አሜሪካዊ ባንከር እና ባለ አረንጓዴ ጃጉዋር መኪና ባለቤት ብቻ ነበር ማለት ነው:: ስለዚህ እሱ ሳይሆን አንተ ነበርክ ፍቅረኛዋ?”
“እኔ እንጃ ፍቅረኛ እባላለሁ ብለሽ ነው?” አላት
ካርተር እስከ አሁን ላንተ እየሰራ ነው?”
ሉዊስም ፊቱን አጥቁሮ “የእኔ ድርጅት
“ከብዙ ጊዜ በፊት ነበር አንቺን ማስወገድ የነበረብኝ” ብሎ ሉዊስ ማውራቱን ቀጠለ “ባይገርምሽ ገና ከሚስቴ ጋር ከመገናኘታችሁ በፊት ነበር
ላስወግድሽ የነበረው:: አየሽ ገና በርክሌ ወደ አንቺ ቢሮ ለቴራፒ ህክምና
ሲመጣ እና ዕብደቱ ሲጀምረው ነበር ላጠፋሽ የነበረው።”
“ካርተርን ነው የምትለኝ?” አለችው ኒኪ በግርምት ተሞልታ። ካርተር
በርክሌይ ከዚህ ጋር ምን የሚያገናኘው ነገር አለው::”
ሉዊስም ፈገግ ብሎ “የእውነት አታውቂም አይደል?”
“አላውቅም” ብላ መለሰችለት፡፡
መልካም ዶክተር ሮበርትስ እንደርሱ ከሆነማ አጭር ተረት ልንገርሻ?
ነገሮችን አገጣጥመሽ እንድትደርሺባቸው እና ዘና እንድትይ አስቤ ነው
ታዲያ ይህንን ተረት የምተርክልሽ፡፡ በድሮ ጊዜ አንድ ሰውዬ ነበር። ይሄ ሰው ግን ወጣት ሳይሆን ከወጣትነት ዕድሜው በትንሹ ያለፈ ሰው ነበር::
ብሎ ሉዊስ የተዋናይ ድምፅ በሆነ መልኩ ትረካውን ቀጠለ፡፡ ድምፁ
የሆነ ደስ የሚል እና ድንዘዝ የሚያደርግ ነገር አለው። ስለዚህም ኒኪ እሱ
እንዴት አድርጎ ወጣቷን አኔን በዚህ መልኩ እንደሚጫወትባት እያሰበች
ትረካውን ማዳመጥ ቀጠለች።
“ሰውዬውን ከሜክሲኮ ሲቲ ከተማ በጥቂት ማይል ርቀት ላይ ከሚገኝ
ጫካ ውስጥ እንደሚገኝ አስቢው፡፡ ቦታው ሞቃት ነው፤ ጨለማ ጊዜ ላይ::
ጨረቃዋ ሙሉ ናት፡፡ ለወራቶች ያህል በጣም የሚያስደስተውን ለስላሳ
የወጣት ገላውን እንደዚያን ቀን አስደስቶት አያውቅም። ያን ዕለት ማታ ሰውዬውን በጣም የተለየ ምርጥ ምሽትን እንዲያሳልፍ ታደርገዋለች::”
ኒኪ ውስጧን ብርድ ብርድ
ሲላት ይታወቃታል። ሰውነቷም
መንቀጥቀጥ ጀመረ። ይህንን ሲያይ ደግሞ የሮድሪጌዝ ፊት በደስታ በራ::
ባለፈው ካርተር በርክሌይን ስታክመው የነገራትን ነገር እያስታወሰች በቀድሞ
ትውስታዋ ውስጥ ተመስጣ ትስመው ጀመር “ቦታው የተመነጠረ ነው::
ምሽት ነበር፡፡ ጭለማ ቢሆንም የጨረቃ ብርሃን ግን ነበር። በጣም ይሞቃል”
የሚለው የካርተር በርክሌይ ድምፅ ጆሮዋ ላይ ደወለባት።
“ስትመጣ አያት” ሮድሪጌዝ ትረካውን ቀጠለ “ሜዳውን እየተደናቀፈች
አቋርጣ ስልኳ ላይ ያለውን የካርታ አድራሻንም ተመለከተች፡፡ ቀይ ፀጉሯ
እሷ ስትራመድ በግራ እና በቀኝ ይወዛወዛል። ረዥም ናት። በጣም ረዥም
ቀጭን ሸንቀጥ ያለች። በእግሮቿ የተሰባበሩትን የዛፍ ቅርንጫፎችን
እየረገጠች ስትመጣ የአዳኝ አይን ውስጥ የገባች ሚዳቆ ትመስል ነበር። ምርጥ ነገር! በጣም ቆንጆ ናት። በዚያ ላይ ደግሞ ገና ለጋ ወጣት? ከእኔ
ጋር ነሽ ዶክተር ሮበርትስ?”
ኒኪ ራሷን በአዎንታ ነቀነቀችለት፡፡ አሁን ሁሉ ነገር ግልፅ ሆነላት። ነገሮቹን ገጣጥማ የሆነ ነገር ላይ ደርሳለች፡፡
“ቻርሎቴ ክላንስ! የምታወራው ስለ ቻርሎቴ ክላንሲ ነው አይደል?”
“በጣም ጎበዝ ነሽ” ብሎ ሮድሪጌዝ ገለፈጠና “ ከሁሉም ነገሯ ሰውዬው
ወደ እሷ እንዲሳብ ያደረገው የዋህነቷ ነበር:: የሆነ እሱ ጋር የሌለው ነገር
ስለነበር ይህንን ነገሯን በጣም ይወድላታል፡፡ ከረዥም ጊዜያት በፊት እሱም ወጣት ነበር፡፡ ግን እንደ እሷ አልነበረም። ሁለቱም የተለያዩ ዓለም ሰዎች ናቸው። ኮከባቸው ሊገጥም የማይገባ ነበር ግን እንዲሁ በድንገት የገጠመ ሆነ። ይሄው ወደ እሱ እየሮጠች ስትመጣ ያያታል።”
“ከዚያስ ምን ተከሰተ?” ብላ ኒኪ ጠየቀችው:: ስትጠይቀው ልክ
ታካሚዎቿን ውስጣቸው ያለውን ነገር እንዲያወጡ በምትጠይቅበት መልኩ
“ከዚያማ ሰውዬው ከመኪናው ውስጥ ወጣ እና ቀስ እያለ ለመቶ ጫማ
ያህል ወደተመነጠረው ቦታ ሄደ። እዚያ ስትደርስ ሰላም ብሎ ሊቀበላት አስቦ
ነው እንግዲህ።” አላት እና ሮድሪጌዝ
የወሲብ ስሜት ተቀስቅሶበታል። ደስ ብሎታል፡፡ ይህንን ነገር ደግሞ
በጣም ይፈልገዋል እና እዚያው ጭለማው ውስጥ እንዳለም
“ቻራ!” ብሎ ጠራት፡፡
“እዚህ ነኝ ፍቅሬ!” አላት ልክ የቻርሎቴን ድምፅ አስመስሎ፡፡ “ከዚያም የተመነጠረው ቦታ ላይ ደረሰች፡፡ ከእሱ 10 ጫማ ርቀት ላይ እያፈረች ቆመች። ወደ እሱ ልትመጣ ስትንቀሳቀስ ግን በእጁ እዚያው እንድትቆም ነገራት፡፡ እዚህ ቦታ ላይ እንደዚህ ቆማ ለዘላለም ሊያስባት እንደሚፈልግም ነገራት።
ይታይሻል አይደል?” አላት ሉዊስ ኒኪን፡፡
“አዎን ትታየኛለች” አለችው እና በመቀጠልም “ግን እኮ ገና 18 ዓመት
የሆናት ልጅ ናት፡፡ ሉዊስ ምንድነው ያደረግካት?” ብላ ጠየቀችው፡፡
እሱም በትንሹ ጎንበስ ብሎ አመስግኖ አሾፈባት እና ትንሽ ስቆም “ልክ ነሽ በድጋሚ ዶክተር ሮበርትስ። ወጣቷ ልጅ ቻርሎቴ ስትሆን ሰውዬው ደግሞ እኔ ነበርኩኝ፡፡ ደርሰሽበታል በእውነት ጎበዝ ነሽ፡፡ ያኔ ከሁለተኛዋ ሚስቴ ጋር ተጋብቼ እኖር ነበር፡፡ ይሄ የሆነው አኔን ከማግኘቴ ከጥቂት ዓመታት በፊት ነበር፡፡ የሚገርም የበጋ ወራት ከቻርሎቴ ጋር በፍቅር
አሳልፌ ነበር፡፡ ግን እንደ አለመታደል ሆኖ ቻርሎቴ መሄድ የማይገባትን
መንገድ ሄዳ ድንበሬን አለፈች፡፡
የጀመርኩትን ነገሮች ከመጨረስ በስተቀር ምንም አይነት ምርጫ አልተወችልኝም ነበር።”
ምን አደረግኳት? አዎን ቀሚሷን እንድታወልቀው ነገርኳት። ልክ እንደ
አኔ ሁሉ እሷም እኔ ጫና እንዳሳድርባት ትፈልጋለች: ትዕዛዞቼን ለመፈፀም
ሁሌም ዝግጁ እና ጉጉም ነበረች” አላት እና ሁኔታውን አስታውሶ ምራቁን
ከዋጠ በኋላ አቤት እጇን ወደ ላይ ከፍ አድርጋ ከጥጥ የተሰራው ልብሷን
ስታወልቅ አሁን ድረስ አይኔ ላይ አለ።
ፖም የሚያካክሉ የሚጣፍጡ መካከለኛ ጡቶች አላት። ልሙጥ ያለው ሆዷም ከፖንቷ በላይ ይታየኛል፡፡ ዋው! ምንኛ ተአምር ነበር መሰለሽ ዶክተር ሮበርት። ከዚያም ደንሺልኝ አልኳት። እሷ ግን በጣም ከማፈሯ የተነሳ ልትደንስልኝ አልቻለችም። ስለዚህ እንድትደንስልኝ ትንሽ እገዛ አደረኩላት፡፡ ከዚህ በፊት የሰው ልጅ በአውቶማቲክ ጠመንጃ በተከታታይ ሲመታ አይተሽ ታውቂያለሽ?” አላት እና አስፈሪ ሳቁን ስቆ “አይተሽ
የምታውቂ አይመስለኝም፤ መሬት ላይ ከመውደቃቸው በፊት ህይወታችው
ወጥቷል፡፡ ግን መሬት ላይ ከመውደቃቸው በፊት አየር ላይ የሚያደርጉት መንቀጥቀጥ፣ መዝለል፣ መንዘፍዘፍ እና እግራቸውን በተለያዩ አቅጣጫዎች በማይታመን ሁኔታ የሚያወናጭፋቸው ነገር እንዴት ደስ ይላል መሰለሽ:: ምን ያደርጋል ታዲያ መጨረሻ ላይ መሬት ሲወድቁ ይሄ ሁሉ አስደናቂ ዳንሳቸው ያበቃል።” ቀጠለናም
ካርተር በርክሌይ የእኔ ባንከር ነበር፡፡ ደስ ይለኝ ነበር። ግን በቃ በጣም ሁሉ ነገሩ የተቋጠረ ሰው ነበር። ለማንኛውም ቻርሎቴ በምታሳየው ትርዒት ትንሽ ይዝናና ብዬ ስላሰብኩኝ ነበር ያን ቀን ይሄው ወደ ቦታው ያመራሁት፡፡ እሱ ስለሆነ ያስተዋወቀን ቢያንስ ትንሽዬ
ያስፈልገዋል፡፡ ስለዚህም እሱን የሚያስደስት ነገር እንዳዘጋጀሁለት ነግሬው ነበር በእኔ መኪና ይዤው የወጣሁት፡፡ ግን ምን ያደርጋል ባየው ነገር መኪና ውስጥ ተቀምጦ በፍርሃት እና በድንጋጤ ይንቀጠቀጥ ጀመር።
ይመስለኛል ቻርሎቴ እንደዋዛ የምፈቅድለት መስሎት ነበር እዚህ
የመጣው።” አላት እና ከት ብሎ ሳቁን ለቀቀው፡፡
“ደግሞስ ለምንድነው በቻርሎቴ እንዲዝናና የምፈቅድለት? ምክንያቱም
የእኔ የሆነ ነገር ሁሉ የእኔ ብቻ ነው”
ኒኪም የነገራትን ነገር ለሰኮንዶች ያህል እያሰበች ዊሊያምስ ከመሞቱ
በፊት የነገራትን ነገር አስታውሳም
“ስለዚህ ካርተር አሜሪካዊ ባንከር እና ባለ አረንጓዴ ጃጉዋር መኪና ባለቤት ብቻ ነበር ማለት ነው:: ስለዚህ እሱ ሳይሆን አንተ ነበርክ ፍቅረኛዋ?”
“እኔ እንጃ ፍቅረኛ እባላለሁ ብለሽ ነው?” አላት
ካርተር እስከ አሁን ላንተ እየሰራ ነው?”
ሉዊስም ፊቱን አጥቁሮ “የእኔ ድርጅት
👍4
እኮ እንደ ባንክ ያለ ድርጅት አይደለም፡፡ ሰዎች በፈለጋቸው ጊዜ ተቀጥረው የሚሰሩበት ባልፈለጉ ጊዜ ደግሞ ለቅቀው የሚወጡበት ድርጅት አይደለም፡፡ አንዴ የእኔን ድርጅት ከተቀላቀልሽ የእኔ ቤተሰብ ሆንሽ ማለት ነው። መውጣት አይቻልም” አላት በጣም ምርር ባለ ድምፅ፡፡...
እንዳለመታደል ሆኖ ከዓመታት በኋላ ካርተር በርክሌይ ሥራውን በአግባቡ የማይሰራ የድርጅታችን አባል ሆኖ አረፈው። በተለይ ደግሞ አንቺ ጋ
መታከም ከጀመረ ጊዜ ጀምሮ”
“ድርጅት ስትል የአደንዛዥ ዕፅ አምራቹን ድርጅትህን ማለትህ ነው?” ብላ ኒኪ ጠየቀችው፡፡
እንደዚያ እንኳን አይደለም ናርኮቲክስ እና የሪል ስቴት ቢዝነሳችን ቅርንጫፎች ናቸው፡፡
አበት!” አለችው ኒኪ ጠንከር አድርጋ። መሞት ካለባት እሱ በሚፈልገው መንገድ መሆን የለበትም፡፡
“ያንተ ሪል ስቴት ቢዝነስ እኮ ከአደንዛዥ ዕፅ ያገኘኸውን ከፍተኛ ትርፍ የምታዘዋውርበት ቢዝነስህ ነው፡፡ ለጋሽነትህም ቢሆን ያው ነው። አንተ
ክሮክ በመሸጥ ነው ህይወትህን የምትኖረው። ስለዚህ አንተ ተራ ኑሮ
በመኖር ላይ ያለህ የአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪ ነህ።” አለችው።
ሉዊስም ራሱን ግራ እና ቀኝ ወዘወዘ፡፡ ምንም የንዴት ፊት አላሳያትም።
ምናልባት ሰዎች ሲገዳደሩ ደስ የሚለው አይነት ሰው ነው።
“ዶክተር ሮበርትስ በመጀመሪያ ደረጃ እኔ ክሮክዲል አይደለም ዋነኛ ንግዴ፡፡ እኔ የማቀርበው ኮኬይን ነው። ምክንያቱም ይህንን ምርት ሰዎች ይፈልጉታል። ኮኬይንን የፈጠርኩት እኔ አይደለሁም። በቃ መንገድ ላይ ነው የተገናኘው::” አላት፡፡
ኒኪ አይኗን አጥብባ በጥላቻ አይን እያየችው “ይሄ ዕፅ ሰዎችን ምን
እንደሚያደርጋቸው መቼስ አይጠፋህም?”
“አውቃለሁ። እኔ ብቻ ሳልሆን ተጠቃሚዎቹም ጭምር ያውቁታል፡፡ እኔ
በደንበኞቼ ምርጫ ተጠያቂ ልሆን አልችልም” አላት እና ያለ ምንም እፍረት
ከመለሰላት በኋላም በርክሌይም በዚህ ጉዳይ ላይ ሊጠየቅ አይችልም፡፡
በምዕራቡ የሀገሪቱ ዳርቻ ላይ ምርጥ የሂሳብ ሠራተኛዬ በመሆን ለብዙ ጊዜ
ቆይቷል፡፡ በቃ ፍራቻው ሳይጀምረው በፊት ምርጥ ሠራተኛዬ በመሆን ለብዙ
ጊዜ ቆይቷል። ከጊዜ በኋላ የሆነ ነገርን መልሶ ማሰብ ተገቢ አይደለም”
“ለማንኛውም በድንገት በርክሌይ ለእነዚህ ደሀ እና የማይረቡ የአደንዛዥ
ዕፅ ተጠቃሚዎች ከልቡ ማዘን ጀመረ።” አለ እና ሮድሪጌዝ በመቀጠልም
“ደግሞ ባይገርምሽ የድርሻውን ሂሳብ ከተቆረጠለት በኋላ መሆኑ ያስቀኛል::
የተሰማውን ሀዘን ለቴራፒስት መዘርገፉን አይጠላውም። ነገር ግን ከእኔ ቢዝነስ የወሰደችውን ሚሊዮን ዶላሮችን መመለስ አይፈልግም። አየሽ በጣም
ስግብግብ እና ደካማ ሆነ። ልክ እዚህ ተሰቅሎ እንዳየሽው ሚ/ር ባደን ነው
ሥራው የሆነብኝ፡፡”
ኒኪም በሀሳቧ ካርተርም የዚህ ቀለበት አካል ነበር ማለት ነው። ለዚህ
ነው ሲያስጠነቅቀኝ የነበረው አለች፡፡ “ባደን እዚህ ውስጥ እንዳለበት ይሄው
ራሱ ነግሮኛል። ደግሞ ሌሎቹ ፓለቲከኞች ወይም ደግሞ ከንቲባው ራሱ እዚህ ውስጥ ይገኛል ብሎ ነበር ዊሊያምስ የነገረኝ? ፖሊሶች እና የበጎ አድራጎት ድርጅቶች በሙሉ ከሮድሪጌዝ የክሮክዲል ትርፍ ተቋዳሽ ናቸው ማለት ነው:: ብላ እያሰበች እያለች
“ዶክተር ሮበርትስ ሎስ አንጀለስ ውስጥ ብዙ ስህተቶችን ስሠራ ነበር፡፡” አላት እና ሮድሪጌዝ ሽጉጡን ተመልክቶም “የመጀመሪያው ስህተቴ በርክሌይን ማመኔ ነው:: ካርተር ብልህ ሰው ቢሆንም ቦጅቧጃ ነገር ነው::ደፋር ሰዎች ደግሞ ለዚህ ቢዝነስ አስፈላጊ ናቸው፡፡ ሁለተኛው ስህተቴ ደግሞ ቫለንቲና ባደን ከባሏ ዊሊ ጋር ሥራን እንድሠራ ስትጠይቀኝ እሺ
ማለቴ ነው፡፡ በዚህም ደግሞ ሌላኛውን ትልቁን ስህተት ሰራሁኝ ማለትም
አንድ ሽባ ግሮልሽ የተባለ ልጅን አንቺን እንዲገድልልኝ መቅጠሬ ነበር።
በዚህም በጣም የሚያስጠላ ስህተትን ሊፈፅም በቃ::”
ይህንን የሰማችው ኒኪም ሽምቅቅ አለች፡፡ ምክንያቱም ብራንዶን እንኳን ሰው ዝምብ ሁሉ የሚገድልበት ጨካኝ ልብ አለው ብላ ልታምን አልቻለችም፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ከማንም በላይ የረዳችውን ወይንም ደግሞ ልትረዳው የሞከረችውን ሴት ሊገድል መስማማቱ ምን ያህል የሮድሪጌዝ አደንዛዥ ዕፅ እሱ ላይ እንደተጫወተበት ነው ያሳያት።
“ልጁ በጣም ሱስ ውስጥ ጠልቆ እንደገባ እና እንደዚህ አይነት ሥራ
ሊሰራ እንደማይችል ማወቅ ነበረብኝ፡፡ ግን ቫለንቲና እሱ ጉዳዩን እንደፈጸመው ክፉኛ አምናበት ነበር። ሱሱ ሰውነቱን በጣም ሳይጎዳው በፊት እሱ እና እሷ ፍቅረኛሞች ነበሩ።” አላት፡፡
“ይህ በፍፁም የማይሆን ነገር ነው። ቫለንቲና እኮ በዕድሜ አያቱ ልትሆን የምትችል ሴት ናት” አለችው ኒኪ፡፡
ሮድሪጌዝም ትከሻውን ሰብቆ “ሱስ እና ፍቅር ውስጥ ምንም አይነት የዕድሜ ገደብ የለም ዶክተር ሮበርትስ። ሟቹ ባልሽ ይሄ ይገባው ነበር፡፡አንቺ ግን አሁንም እርጥብ ነሽ፡፡ ለማንኛውም ይህቺ ሸርሙጣ አሮጊት የእሷ
የሆነ ፍቅረኛ ለእሷ ብሎ ሰው የሚገድልላት ሀሳብ በራሱ መስጧት ነበር
ብራንዶን ዶክተር ሮበርትስን ያውቃታል፤ የእሷ ችግር የለውም ዕድሉን ስጠው ብላ ነበር በጉዳዩ ላይ ያሳመነችኝ፡፡ እኔም በወቅቱ ገና ከጓደኞቼ ጋር ሥራ የጀመርኩበት ጊዜ ስለነበር እነርሱን ለማስደሰት ብዬ የእሷን ሀሳብ
ተቀበልኩኝ፡፡ ይሄ ግን ድድብና ነበር” ብሎ ሉዊስ ጭንቅላቱን በምሬት ወዘወዘ፡ እና “በጣም አሰቃቂ ነገር እኮ ነው። በቃ ግሮልሽ ማድረግ የነበረበት ነገር ሲኖር አንቺን ከቢሮሽ እስክትወጪ ድረስ ጠብቆ ልብሽ ላይ ጩቤ መሰካት ብቻ ነበር። ማለቴ ይሄን ማድረግ እንዴት ነው የሚከብደው? እናም የዚያን ምሽት ሊዛ ፍላንገን ያንቺን የዝናብ ኮት ደርባ ካንቺ ቢሮ ስትወጣ ተመልክቶ ተከተላት እና ገደላት፡፡ ወይም ደግሞ ልክ እንደ ጨርቅ
ቆራረጣት። ምን አይነት ስህተት እንደሆነ ይገባሻል?
“ብራንዶን ልጅቷን ከገደላት በኋላ የእኔ ሰዎች ሬሳዋን የማፅዳት ሥራቸውን ሲሠሩም ስህተት ተፈጠረ። በችኮላ ሥራቸውን ስለሰሩም ጥፍሯ
ውስጥ የዚያን በክሮክ ሱስ የነተበውን እና የበሰበሰውን የቆዳ ህዋስ ሳያፀዱ
ቀሩ። ፖሊሶችም የህዋሱን ባለቤት በዲ.ኤን.ኤው ሊለዩት ቻሉ፡፡ ስለሆነም
የግድያ ምርመራ እና ሚዲያዎች ዜናውን በማራገብ ቡድኖች እና ብራንዶንን
ተስፋ እንዲቆርጡ አደረጓቸው:: በዚህ ሁሉ ነገር ውስጥ ግን አንቺ በህይወት
መኖር ቀጠልሽ፤ በተለይ ደግሞ የኔን አኔን እያገኘሽ”
ብሎ የሚስቱን ሥም ከጠራ በኋላ ሙሉ ፊቱ ተቀያየረ፡፡ በድንገትም ዘና ብሎ የሚያወራ ድምፁ ተቀየረ እና ጥላቻውን በደንብ በሚገልፅ መልኩ
እያፈጠጠባትም ሎስ አንጀለስ ውስጥ ከሚገኙ ከ1000 በላይ ቴራፒስቶች ውስጥ ሚስቴ አንቺ ጋ መጥታ ህክምና መጀመሯ ይገርመኛል፡፡ አይገርምም? ባንከሬ የሆዱን ክፋት ለማውራት የመረጣት ሴትን እሷም መምረጧ ግን
አይደንቅሽም?”
ላይገርም ይችላል ምናልባት ካርተር እኔ ጋ መጥቶ ህክምናውን እንደሚከታተል የሚያውቅ ሰው ይበልጥ አደጋ ውስጥ ለመክተት አስቦ ወደ እኔ ጠቁሟት ሊሆን ይችላል ስትል አሰበች ኒኪ፡፡
በተጨማሪ ብራንዶን ግሮልሽ እሷን ለመግደል ገንዘብ መቀበሉን እና
በስህተት ምስኪኗ ሊዛን መግደሉ ምን አይነት አጋጣሚ ሊሆን ይችላል?
እንድትረዳው እና ይቅርታ እንድታደርግለት ጭምር ለምኗት አልነበር?ድንቄም ይቅርታ! እያለች በውስጧ ተብሰለሰለች፡፡ አእምሮዋን ያነበበ ይመስል
“አትሳሳች” አላት እና ሉዊስ ከሀሳቧ አናጠባት፡፡ “ገና ካርተር ወደ አንቺ
ቢሮ መጥቶ ህክምናውን መውሰድ የጀመረ ቀን ላይ ነበር ያንቺ የሞት ወረቀት የተፈረመው ግን አየሽ ያኔ ጉዳዩ በግል የሚመለከተኝ አልነበረም።ነገር ግን አኔን ማግኘት ስትጀምሪ
እንዳለመታደል ሆኖ ከዓመታት በኋላ ካርተር በርክሌይ ሥራውን በአግባቡ የማይሰራ የድርጅታችን አባል ሆኖ አረፈው። በተለይ ደግሞ አንቺ ጋ
መታከም ከጀመረ ጊዜ ጀምሮ”
“ድርጅት ስትል የአደንዛዥ ዕፅ አምራቹን ድርጅትህን ማለትህ ነው?” ብላ ኒኪ ጠየቀችው፡፡
እንደዚያ እንኳን አይደለም ናርኮቲክስ እና የሪል ስቴት ቢዝነሳችን ቅርንጫፎች ናቸው፡፡
አበት!” አለችው ኒኪ ጠንከር አድርጋ። መሞት ካለባት እሱ በሚፈልገው መንገድ መሆን የለበትም፡፡
“ያንተ ሪል ስቴት ቢዝነስ እኮ ከአደንዛዥ ዕፅ ያገኘኸውን ከፍተኛ ትርፍ የምታዘዋውርበት ቢዝነስህ ነው፡፡ ለጋሽነትህም ቢሆን ያው ነው። አንተ
ክሮክ በመሸጥ ነው ህይወትህን የምትኖረው። ስለዚህ አንተ ተራ ኑሮ
በመኖር ላይ ያለህ የአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪ ነህ።” አለችው።
ሉዊስም ራሱን ግራ እና ቀኝ ወዘወዘ፡፡ ምንም የንዴት ፊት አላሳያትም።
ምናልባት ሰዎች ሲገዳደሩ ደስ የሚለው አይነት ሰው ነው።
“ዶክተር ሮበርትስ በመጀመሪያ ደረጃ እኔ ክሮክዲል አይደለም ዋነኛ ንግዴ፡፡ እኔ የማቀርበው ኮኬይን ነው። ምክንያቱም ይህንን ምርት ሰዎች ይፈልጉታል። ኮኬይንን የፈጠርኩት እኔ አይደለሁም። በቃ መንገድ ላይ ነው የተገናኘው::” አላት፡፡
ኒኪ አይኗን አጥብባ በጥላቻ አይን እያየችው “ይሄ ዕፅ ሰዎችን ምን
እንደሚያደርጋቸው መቼስ አይጠፋህም?”
“አውቃለሁ። እኔ ብቻ ሳልሆን ተጠቃሚዎቹም ጭምር ያውቁታል፡፡ እኔ
በደንበኞቼ ምርጫ ተጠያቂ ልሆን አልችልም” አላት እና ያለ ምንም እፍረት
ከመለሰላት በኋላም በርክሌይም በዚህ ጉዳይ ላይ ሊጠየቅ አይችልም፡፡
በምዕራቡ የሀገሪቱ ዳርቻ ላይ ምርጥ የሂሳብ ሠራተኛዬ በመሆን ለብዙ ጊዜ
ቆይቷል፡፡ በቃ ፍራቻው ሳይጀምረው በፊት ምርጥ ሠራተኛዬ በመሆን ለብዙ
ጊዜ ቆይቷል። ከጊዜ በኋላ የሆነ ነገርን መልሶ ማሰብ ተገቢ አይደለም”
“ለማንኛውም በድንገት በርክሌይ ለእነዚህ ደሀ እና የማይረቡ የአደንዛዥ
ዕፅ ተጠቃሚዎች ከልቡ ማዘን ጀመረ።” አለ እና ሮድሪጌዝ በመቀጠልም
“ደግሞ ባይገርምሽ የድርሻውን ሂሳብ ከተቆረጠለት በኋላ መሆኑ ያስቀኛል::
የተሰማውን ሀዘን ለቴራፒስት መዘርገፉን አይጠላውም። ነገር ግን ከእኔ ቢዝነስ የወሰደችውን ሚሊዮን ዶላሮችን መመለስ አይፈልግም። አየሽ በጣም
ስግብግብ እና ደካማ ሆነ። ልክ እዚህ ተሰቅሎ እንዳየሽው ሚ/ር ባደን ነው
ሥራው የሆነብኝ፡፡”
ኒኪም በሀሳቧ ካርተርም የዚህ ቀለበት አካል ነበር ማለት ነው። ለዚህ
ነው ሲያስጠነቅቀኝ የነበረው አለች፡፡ “ባደን እዚህ ውስጥ እንዳለበት ይሄው
ራሱ ነግሮኛል። ደግሞ ሌሎቹ ፓለቲከኞች ወይም ደግሞ ከንቲባው ራሱ እዚህ ውስጥ ይገኛል ብሎ ነበር ዊሊያምስ የነገረኝ? ፖሊሶች እና የበጎ አድራጎት ድርጅቶች በሙሉ ከሮድሪጌዝ የክሮክዲል ትርፍ ተቋዳሽ ናቸው ማለት ነው:: ብላ እያሰበች እያለች
“ዶክተር ሮበርትስ ሎስ አንጀለስ ውስጥ ብዙ ስህተቶችን ስሠራ ነበር፡፡” አላት እና ሮድሪጌዝ ሽጉጡን ተመልክቶም “የመጀመሪያው ስህተቴ በርክሌይን ማመኔ ነው:: ካርተር ብልህ ሰው ቢሆንም ቦጅቧጃ ነገር ነው::ደፋር ሰዎች ደግሞ ለዚህ ቢዝነስ አስፈላጊ ናቸው፡፡ ሁለተኛው ስህተቴ ደግሞ ቫለንቲና ባደን ከባሏ ዊሊ ጋር ሥራን እንድሠራ ስትጠይቀኝ እሺ
ማለቴ ነው፡፡ በዚህም ደግሞ ሌላኛውን ትልቁን ስህተት ሰራሁኝ ማለትም
አንድ ሽባ ግሮልሽ የተባለ ልጅን አንቺን እንዲገድልልኝ መቅጠሬ ነበር።
በዚህም በጣም የሚያስጠላ ስህተትን ሊፈፅም በቃ::”
ይህንን የሰማችው ኒኪም ሽምቅቅ አለች፡፡ ምክንያቱም ብራንዶን እንኳን ሰው ዝምብ ሁሉ የሚገድልበት ጨካኝ ልብ አለው ብላ ልታምን አልቻለችም፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ከማንም በላይ የረዳችውን ወይንም ደግሞ ልትረዳው የሞከረችውን ሴት ሊገድል መስማማቱ ምን ያህል የሮድሪጌዝ አደንዛዥ ዕፅ እሱ ላይ እንደተጫወተበት ነው ያሳያት።
“ልጁ በጣም ሱስ ውስጥ ጠልቆ እንደገባ እና እንደዚህ አይነት ሥራ
ሊሰራ እንደማይችል ማወቅ ነበረብኝ፡፡ ግን ቫለንቲና እሱ ጉዳዩን እንደፈጸመው ክፉኛ አምናበት ነበር። ሱሱ ሰውነቱን በጣም ሳይጎዳው በፊት እሱ እና እሷ ፍቅረኛሞች ነበሩ።” አላት፡፡
“ይህ በፍፁም የማይሆን ነገር ነው። ቫለንቲና እኮ በዕድሜ አያቱ ልትሆን የምትችል ሴት ናት” አለችው ኒኪ፡፡
ሮድሪጌዝም ትከሻውን ሰብቆ “ሱስ እና ፍቅር ውስጥ ምንም አይነት የዕድሜ ገደብ የለም ዶክተር ሮበርትስ። ሟቹ ባልሽ ይሄ ይገባው ነበር፡፡አንቺ ግን አሁንም እርጥብ ነሽ፡፡ ለማንኛውም ይህቺ ሸርሙጣ አሮጊት የእሷ
የሆነ ፍቅረኛ ለእሷ ብሎ ሰው የሚገድልላት ሀሳብ በራሱ መስጧት ነበር
ብራንዶን ዶክተር ሮበርትስን ያውቃታል፤ የእሷ ችግር የለውም ዕድሉን ስጠው ብላ ነበር በጉዳዩ ላይ ያሳመነችኝ፡፡ እኔም በወቅቱ ገና ከጓደኞቼ ጋር ሥራ የጀመርኩበት ጊዜ ስለነበር እነርሱን ለማስደሰት ብዬ የእሷን ሀሳብ
ተቀበልኩኝ፡፡ ይሄ ግን ድድብና ነበር” ብሎ ሉዊስ ጭንቅላቱን በምሬት ወዘወዘ፡ እና “በጣም አሰቃቂ ነገር እኮ ነው። በቃ ግሮልሽ ማድረግ የነበረበት ነገር ሲኖር አንቺን ከቢሮሽ እስክትወጪ ድረስ ጠብቆ ልብሽ ላይ ጩቤ መሰካት ብቻ ነበር። ማለቴ ይሄን ማድረግ እንዴት ነው የሚከብደው? እናም የዚያን ምሽት ሊዛ ፍላንገን ያንቺን የዝናብ ኮት ደርባ ካንቺ ቢሮ ስትወጣ ተመልክቶ ተከተላት እና ገደላት፡፡ ወይም ደግሞ ልክ እንደ ጨርቅ
ቆራረጣት። ምን አይነት ስህተት እንደሆነ ይገባሻል?
“ብራንዶን ልጅቷን ከገደላት በኋላ የእኔ ሰዎች ሬሳዋን የማፅዳት ሥራቸውን ሲሠሩም ስህተት ተፈጠረ። በችኮላ ሥራቸውን ስለሰሩም ጥፍሯ
ውስጥ የዚያን በክሮክ ሱስ የነተበውን እና የበሰበሰውን የቆዳ ህዋስ ሳያፀዱ
ቀሩ። ፖሊሶችም የህዋሱን ባለቤት በዲ.ኤን.ኤው ሊለዩት ቻሉ፡፡ ስለሆነም
የግድያ ምርመራ እና ሚዲያዎች ዜናውን በማራገብ ቡድኖች እና ብራንዶንን
ተስፋ እንዲቆርጡ አደረጓቸው:: በዚህ ሁሉ ነገር ውስጥ ግን አንቺ በህይወት
መኖር ቀጠልሽ፤ በተለይ ደግሞ የኔን አኔን እያገኘሽ”
ብሎ የሚስቱን ሥም ከጠራ በኋላ ሙሉ ፊቱ ተቀያየረ፡፡ በድንገትም ዘና ብሎ የሚያወራ ድምፁ ተቀየረ እና ጥላቻውን በደንብ በሚገልፅ መልኩ
እያፈጠጠባትም ሎስ አንጀለስ ውስጥ ከሚገኙ ከ1000 በላይ ቴራፒስቶች ውስጥ ሚስቴ አንቺ ጋ መጥታ ህክምና መጀመሯ ይገርመኛል፡፡ አይገርምም? ባንከሬ የሆዱን ክፋት ለማውራት የመረጣት ሴትን እሷም መምረጧ ግን
አይደንቅሽም?”
ላይገርም ይችላል ምናልባት ካርተር እኔ ጋ መጥቶ ህክምናውን እንደሚከታተል የሚያውቅ ሰው ይበልጥ አደጋ ውስጥ ለመክተት አስቦ ወደ እኔ ጠቁሟት ሊሆን ይችላል ስትል አሰበች ኒኪ፡፡
በተጨማሪ ብራንዶን ግሮልሽ እሷን ለመግደል ገንዘብ መቀበሉን እና
በስህተት ምስኪኗ ሊዛን መግደሉ ምን አይነት አጋጣሚ ሊሆን ይችላል?
እንድትረዳው እና ይቅርታ እንድታደርግለት ጭምር ለምኗት አልነበር?ድንቄም ይቅርታ! እያለች በውስጧ ተብሰለሰለች፡፡ አእምሮዋን ያነበበ ይመስል
“አትሳሳች” አላት እና ሉዊስ ከሀሳቧ አናጠባት፡፡ “ገና ካርተር ወደ አንቺ
ቢሮ መጥቶ ህክምናውን መውሰድ የጀመረ ቀን ላይ ነበር ያንቺ የሞት ወረቀት የተፈረመው ግን አየሽ ያኔ ጉዳዩ በግል የሚመለከተኝ አልነበረም።ነገር ግን አኔን ማግኘት ስትጀምሪ
👍2
ነገሮች ሙሉ በሙሉ ተለወጡ።” አላት አይኖቹን አጥብቦ እየተመለከታት ቀጠለናም “ዶክተር ሮበርትስ በጣም ነው የጠላሁሽ” አላትና ሮድሪጌዝ ስለ አኔ ማውራቱን ቀጠለ። እንዴት በመኪናዋ እና በኪስ ማስታወሻዋ ላይ የመቅጂያ መሳሪያ ገጥሞ ሲሰልላት እንደቆየ ነገራት። በዚህም የእሱን አኔን ለመቀማት ብላ እንዴት አድርጋ አዕምሮዋን ስትመርዛት እንደነበር በማወቁ የተነሳ እጅግ እንደጠላት ጭምር ነገራት::
ሉዊስ ስለ አኔ እያወራት እያለም ኒኪ ልታመልጥበት የምትችልበት መንገድ እንዳለ ማሰብ ጀመረች። ሉዊስ ሮድሪጌዝ ትንሽ አዕምሮው የተወሳሰበበት ሰው እንደሆነ ለማየት በቅታለች። ይህንን ደግሞ ልትጠቀምበት ትችላለች። ያለበለዚያማ ምኑን ሳይኮሎጂስት ሆነችው ታዲያ? ማውራቱን እንዲቀጥል እና ለራሱ የሚሰጠው ከፍተኛ ግምትም
ጊዜን እንደሚሰጣት ጭምር አሰበች። በህይወት ለመቆየት እስከፈለገች ድረስ
ደግሞ አዘናግታው ሽጉጡን ከእጁ ላይ ማስጣል ይኖርባታል።
ከዚያስ? መሮጥ ይኖርባታል። ወዴት? ምናልባት ሁለቱ ሰዎች አኔን ይዘው በወረዱበት አሳንሰር ወደ ታች መውረድ ትችል ይሆናል። ግን ደግሞ
ሽጉጡን አስጥላው እሷ እጅ ውስጥ ማስገባት ከቻለች ያኔ አሽናፊ ትሆናለች፡፡ ያም ሆኖ ግን ኮሪደሩ ላይም ሆነ በኮሪደሩ ግራ ቀኝ ከሚገኙት
ቢሮዎች ውስጥ የእሱን ሽጉጥ ለማስጣል የሚረዷት ነገሮች የሉም።
ቦርሳዋን እንኳን አልያዘችም፡፡ እጇ ላይ የሚገኘውም የመኪናዋ ቁልፍ ብቻ
ነው፡፡
በይበልጥ በትክክለኛዋ አዕምሮዋ ስለማምለጥ ባሰበች ቁጥር ውስጧ
የነበረው መረጋጋት እየጠፋ እና ፍርሃቷም እየተቆጣጠራት መጣ፡፡ አሁን ለመሞት ዝግጁ አይደለችም፡፡ በተለይ ደግሞ ዛሬ ማታ ያውም በአንድ በሰው ስቃይ በሚደሰት ሰው እጅ:: ስለዚህ ከዚህ ሞት የምታመልጥበት መንገድ የግድ ሊኖር ይገባል።
ጉድማን ወደ ሳን ጁሊያን መንገድ ሲታጠፍ ሸሚዙ በላብ ከመበስበሱም
በላይ የእጁ ላብም የመኪናውን መሪ እንዲያሟልጭበት አድርጎታል፡፡
ፍርሃት ሆዱን አሞታል፡፡ ፊቱንም አገርጥቶታል፡፡ አፉ ክው ብሎ
ከመድረቁም በላይ የልቡ ምት በጣም ስለፈጠነበት መተንፈስ አቅቶታል፡፡
በውስጡ ያለው አድሬናሊን ግን ፍርሃቱን አሸንፎ እርምጃ እንዲወስድ አስገድዶታል። መኪናውን አቆመና ከመኪናው ወርዶ ሽጉጡን በማውጣት
እየሮጠ ወደ ህንፃው መጠጋት ጀመረ። በውስጡ የሚገኘው በህይወት
የመቆየት ደመነፍሱ አሸናፊ እንደሚሆን ነግሮታል፡፡ ይህም ፍርሃቱን በግድም ቢሆን እንዲውጠው አድርጎታል።
ይሄ ነው ጉዳዩ። አድርግ ወይንም ሙት!
ህይወት ወይንም ሞት!
መንገዱ ጭር ብሏል። አንዳንድ ከሴቶች ልብስ ማምረቻ የሚወጡ አርፋጅ ሰራተኞች ስምንተኛው ጎዳና ላይ ወደሚገኘው ባቡር ጣቢያ እያመሩ
ይገኛሉ። ማንም ሰው ጉድማን መኪናውን አቁሞ ወደ መጋዘኑ ህንፃ ሲያመራ ጉዳዬ አላለውም፡፡ ከህንፃው ሰላሳ ያርድ ሲቀረው ግን ሁለቱ ጥቁር በ ሙሉ ልብስ የለበሱ ሰዎች አንዲት ሴትን መሀል አድርገው ሲመጡ ተመለከታቸው እና ተደበቀ፡፡ ከተደበቀበት ቦታ ሆኖ ሲመለከት ሴቷ አኔ ቤታማን መሆኗን አወቀ፡፡ ሰዎቹ አኔን አንድ መኪና ውስጥ አስገቧት እና ከመኪናው ሹፌር ጋር ጥቂት አውርተው እንዳበቁም መኪናው ወደ ሌላኛው የሳን ጁሊያን መንገድ ጫፍ በፍጥነት መንቀሳቀስ ጀመረ። ሁለቱ ሰዎችም መኪናው ከተንቀሳቀስ በኋላ ሽጉጣቸውን አወጡ። በህንፃው በተለያየ
አቅጣጫም ተንቀሳቀሱ፡፡ ከሁለቱ ውስጥ አንደኛው ሰው ከህንፃው ፊት ለፊት ቁጢጥ ብሎ አካባቢውን መቃኘት ጀመረ፡፡
ጉድማን ከሁለቱ አንደኛው ሰው እጅ ላይ ያየው ደም የማን ሊሆን እንደሚችል ማሰብ ጀመረ:: ገና ፖሊስ ጣቢያ ሆኖ የገመተው ነገር ትክክል እንደሆነ እርግጠኛ ሆኗል፡፡ አዎን ሉዊስ ሮድሪጌዝ እዚህ ህንፃ ውስጥ ይገኛል፡፡ ሉዊስ ደግሞ ዶክተር ሮበርትስን በፍፁም እንደማይምራት ያውቃል።
ሽጉጡን በእጁ ጨብጦ ምን ማድረግ እንደሚገባው ማውጣት እና ማወረዱን ቀጠለ። እሱ ብቻውን ነው ሮድሪጌዝ ደግሞ ቢያንስ ሁለት ወይም ከሁለት በላይ ሰዎች አሉት፡፡ ተጨማሪ ሀይል እንዲመጣለት ማድረግም ይችላል፡፡ ትክክለኛው አሰራሩም እንደዚያ ነው፡፡ ሁለቱን የሮድሪጌዝን ሰዎች አሸንፎ ወደ ውስጥ መግባትን ማሰብ ደግሞ እጅግ አደገኛ ቁማር ነው::
ምናልባት ህንፃው ውስጥ ብዙ የሮድሪጌዝ ሰዎችን ሊያገኝ ይችላል። ይሄ
ደግሞ ሞትን መሻት ነው የሚሆነው።
ዙሪያውን ሲቃኝ በቀኝ በኩል ቀጭን መተላለፊያ እንዳለ ለማየት ቻለ። ስፋቱ ሞተር ሳይክል ብቻ ነው ሊያሳልፍ የሚችለው፡፡ ምናልባትም ህንፃውን
ለመጠገን ሲባል የተተው ቦታ ሊሆን ይችላል። እንደምንም ተደብቆ ከጠባቡ
ቆጣሪዎችን ተመለከተ። ወለሉ ላይም የትቦ መድፈኛ የሆነ ፍርግርግ ብረትን
መተላለፊያ ውስጥ ገባ፡፡ ግድግዳው ላይም ሁለት የተቆለፈባቸው የመብራት
ቆጣሪዎች ተመለከተ።ወለሉ ላይም የትቦ መድፈኛ የሆነ ፍርግርግ ብረትን
ተመለከተ፡፡ ብረቱን በሀይል ወደ ላይ ሲስበውም ወደ ህንፃው የምድር ክፍል
የሚያስገባው ጠባብ ዋሻ መሰል ቱቦን ለማየት ቻለ፡፡
ወጥመድ ውስጥ የገባ አይጥ አይነት ስሜት እንዲሰማው ስለሚያደርጉት
ጉድማን እንደዚህ ያሉ ጠባብ ቦታዎችን
አይወድም ለማንኛውም ብረቱን
በሀይል ወደ ላይ ሲስበውም ወደ ህንፃው የምድር ክፍል የሚያስገባ ጠባብ
ዋሻ መሰል ቱቦን ለማየት ቻለ።
ለማንኛውም ብረቱን ሲስብ ድምፁ ስለተሰ ውጪ ካሉት ሁለት ሰዎች አንዱ ወደ እዚህ ቦታ መምጣቱ አይቀርም::
ሲመጣ እና ጉድማንን ሲያገኘው ደግሞ ምንምንኩዋ ሳይጠይቀው እንደሚተኩስበት እርግጠኛ ነው፡፡ ይሄ በራሱ ደግሞ ሌላ ችግርን መፍጠር ስለሆነ ብረቱን እንደያዘ ወደ ውስጥ ገባ እና በላዩ ላይ ብረቱን ዘጋ፡፡
በጠባቡ ዋሻ መሰል ቱቦ ወደ ታች እየወረደም በውስጡ በኒኪ ሮበርትስ
መናደድ ጀመረ፡፡
ደደብ አመፀኛ ሴት! ለምንድነው እዚህ ድረስ ብቻዋን የመጣችው? የአኔ
ቤታማንን ትዕዛዝ ሰምታ እና እንደ በግ ለመታረድ እንዴት እዚህ ነገር ውስጥ ዘልላ ትገባለች? የዴሪክ ዊሊያምስ ሞት በራሱ እንዴት ማስጠንቀቂያ
ሊሆናት አልቻለም እያለ በውስጡ ይቃጠል ጀመር፡፡
ኒኪ ቆንጆ እና ብልህ ሴት ልትሆን ትችል ይሆናል፤ ነገር ግን ራሷን ልትወጣበት ከማትችለው ጥልቅ ውሃ ውስጥ ነው የተከተተችው፡፡ የውሃውን ጥልቀት ደግሞ በደንብ የሚያውቀው ጉድማን ነው::....
✨ይቀጥላል✨
ሉዊስ ስለ አኔ እያወራት እያለም ኒኪ ልታመልጥበት የምትችልበት መንገድ እንዳለ ማሰብ ጀመረች። ሉዊስ ሮድሪጌዝ ትንሽ አዕምሮው የተወሳሰበበት ሰው እንደሆነ ለማየት በቅታለች። ይህንን ደግሞ ልትጠቀምበት ትችላለች። ያለበለዚያማ ምኑን ሳይኮሎጂስት ሆነችው ታዲያ? ማውራቱን እንዲቀጥል እና ለራሱ የሚሰጠው ከፍተኛ ግምትም
ጊዜን እንደሚሰጣት ጭምር አሰበች። በህይወት ለመቆየት እስከፈለገች ድረስ
ደግሞ አዘናግታው ሽጉጡን ከእጁ ላይ ማስጣል ይኖርባታል።
ከዚያስ? መሮጥ ይኖርባታል። ወዴት? ምናልባት ሁለቱ ሰዎች አኔን ይዘው በወረዱበት አሳንሰር ወደ ታች መውረድ ትችል ይሆናል። ግን ደግሞ
ሽጉጡን አስጥላው እሷ እጅ ውስጥ ማስገባት ከቻለች ያኔ አሽናፊ ትሆናለች፡፡ ያም ሆኖ ግን ኮሪደሩ ላይም ሆነ በኮሪደሩ ግራ ቀኝ ከሚገኙት
ቢሮዎች ውስጥ የእሱን ሽጉጥ ለማስጣል የሚረዷት ነገሮች የሉም።
ቦርሳዋን እንኳን አልያዘችም፡፡ እጇ ላይ የሚገኘውም የመኪናዋ ቁልፍ ብቻ
ነው፡፡
በይበልጥ በትክክለኛዋ አዕምሮዋ ስለማምለጥ ባሰበች ቁጥር ውስጧ
የነበረው መረጋጋት እየጠፋ እና ፍርሃቷም እየተቆጣጠራት መጣ፡፡ አሁን ለመሞት ዝግጁ አይደለችም፡፡ በተለይ ደግሞ ዛሬ ማታ ያውም በአንድ በሰው ስቃይ በሚደሰት ሰው እጅ:: ስለዚህ ከዚህ ሞት የምታመልጥበት መንገድ የግድ ሊኖር ይገባል።
ጉድማን ወደ ሳን ጁሊያን መንገድ ሲታጠፍ ሸሚዙ በላብ ከመበስበሱም
በላይ የእጁ ላብም የመኪናውን መሪ እንዲያሟልጭበት አድርጎታል፡፡
ፍርሃት ሆዱን አሞታል፡፡ ፊቱንም አገርጥቶታል፡፡ አፉ ክው ብሎ
ከመድረቁም በላይ የልቡ ምት በጣም ስለፈጠነበት መተንፈስ አቅቶታል፡፡
በውስጡ ያለው አድሬናሊን ግን ፍርሃቱን አሸንፎ እርምጃ እንዲወስድ አስገድዶታል። መኪናውን አቆመና ከመኪናው ወርዶ ሽጉጡን በማውጣት
እየሮጠ ወደ ህንፃው መጠጋት ጀመረ። በውስጡ የሚገኘው በህይወት
የመቆየት ደመነፍሱ አሸናፊ እንደሚሆን ነግሮታል፡፡ ይህም ፍርሃቱን በግድም ቢሆን እንዲውጠው አድርጎታል።
ይሄ ነው ጉዳዩ። አድርግ ወይንም ሙት!
ህይወት ወይንም ሞት!
መንገዱ ጭር ብሏል። አንዳንድ ከሴቶች ልብስ ማምረቻ የሚወጡ አርፋጅ ሰራተኞች ስምንተኛው ጎዳና ላይ ወደሚገኘው ባቡር ጣቢያ እያመሩ
ይገኛሉ። ማንም ሰው ጉድማን መኪናውን አቁሞ ወደ መጋዘኑ ህንፃ ሲያመራ ጉዳዬ አላለውም፡፡ ከህንፃው ሰላሳ ያርድ ሲቀረው ግን ሁለቱ ጥቁር በ ሙሉ ልብስ የለበሱ ሰዎች አንዲት ሴትን መሀል አድርገው ሲመጡ ተመለከታቸው እና ተደበቀ፡፡ ከተደበቀበት ቦታ ሆኖ ሲመለከት ሴቷ አኔ ቤታማን መሆኗን አወቀ፡፡ ሰዎቹ አኔን አንድ መኪና ውስጥ አስገቧት እና ከመኪናው ሹፌር ጋር ጥቂት አውርተው እንዳበቁም መኪናው ወደ ሌላኛው የሳን ጁሊያን መንገድ ጫፍ በፍጥነት መንቀሳቀስ ጀመረ። ሁለቱ ሰዎችም መኪናው ከተንቀሳቀስ በኋላ ሽጉጣቸውን አወጡ። በህንፃው በተለያየ
አቅጣጫም ተንቀሳቀሱ፡፡ ከሁለቱ ውስጥ አንደኛው ሰው ከህንፃው ፊት ለፊት ቁጢጥ ብሎ አካባቢውን መቃኘት ጀመረ፡፡
ጉድማን ከሁለቱ አንደኛው ሰው እጅ ላይ ያየው ደም የማን ሊሆን እንደሚችል ማሰብ ጀመረ:: ገና ፖሊስ ጣቢያ ሆኖ የገመተው ነገር ትክክል እንደሆነ እርግጠኛ ሆኗል፡፡ አዎን ሉዊስ ሮድሪጌዝ እዚህ ህንፃ ውስጥ ይገኛል፡፡ ሉዊስ ደግሞ ዶክተር ሮበርትስን በፍፁም እንደማይምራት ያውቃል።
ሽጉጡን በእጁ ጨብጦ ምን ማድረግ እንደሚገባው ማውጣት እና ማወረዱን ቀጠለ። እሱ ብቻውን ነው ሮድሪጌዝ ደግሞ ቢያንስ ሁለት ወይም ከሁለት በላይ ሰዎች አሉት፡፡ ተጨማሪ ሀይል እንዲመጣለት ማድረግም ይችላል፡፡ ትክክለኛው አሰራሩም እንደዚያ ነው፡፡ ሁለቱን የሮድሪጌዝን ሰዎች አሸንፎ ወደ ውስጥ መግባትን ማሰብ ደግሞ እጅግ አደገኛ ቁማር ነው::
ምናልባት ህንፃው ውስጥ ብዙ የሮድሪጌዝ ሰዎችን ሊያገኝ ይችላል። ይሄ
ደግሞ ሞትን መሻት ነው የሚሆነው።
ዙሪያውን ሲቃኝ በቀኝ በኩል ቀጭን መተላለፊያ እንዳለ ለማየት ቻለ። ስፋቱ ሞተር ሳይክል ብቻ ነው ሊያሳልፍ የሚችለው፡፡ ምናልባትም ህንፃውን
ለመጠገን ሲባል የተተው ቦታ ሊሆን ይችላል። እንደምንም ተደብቆ ከጠባቡ
ቆጣሪዎችን ተመለከተ። ወለሉ ላይም የትቦ መድፈኛ የሆነ ፍርግርግ ብረትን
መተላለፊያ ውስጥ ገባ፡፡ ግድግዳው ላይም ሁለት የተቆለፈባቸው የመብራት
ቆጣሪዎች ተመለከተ።ወለሉ ላይም የትቦ መድፈኛ የሆነ ፍርግርግ ብረትን
ተመለከተ፡፡ ብረቱን በሀይል ወደ ላይ ሲስበውም ወደ ህንፃው የምድር ክፍል
የሚያስገባው ጠባብ ዋሻ መሰል ቱቦን ለማየት ቻለ፡፡
ወጥመድ ውስጥ የገባ አይጥ አይነት ስሜት እንዲሰማው ስለሚያደርጉት
ጉድማን እንደዚህ ያሉ ጠባብ ቦታዎችን
አይወድም ለማንኛውም ብረቱን
በሀይል ወደ ላይ ሲስበውም ወደ ህንፃው የምድር ክፍል የሚያስገባ ጠባብ
ዋሻ መሰል ቱቦን ለማየት ቻለ።
ለማንኛውም ብረቱን ሲስብ ድምፁ ስለተሰ ውጪ ካሉት ሁለት ሰዎች አንዱ ወደ እዚህ ቦታ መምጣቱ አይቀርም::
ሲመጣ እና ጉድማንን ሲያገኘው ደግሞ ምንምንኩዋ ሳይጠይቀው እንደሚተኩስበት እርግጠኛ ነው፡፡ ይሄ በራሱ ደግሞ ሌላ ችግርን መፍጠር ስለሆነ ብረቱን እንደያዘ ወደ ውስጥ ገባ እና በላዩ ላይ ብረቱን ዘጋ፡፡
በጠባቡ ዋሻ መሰል ቱቦ ወደ ታች እየወረደም በውስጡ በኒኪ ሮበርትስ
መናደድ ጀመረ፡፡
ደደብ አመፀኛ ሴት! ለምንድነው እዚህ ድረስ ብቻዋን የመጣችው? የአኔ
ቤታማንን ትዕዛዝ ሰምታ እና እንደ በግ ለመታረድ እንዴት እዚህ ነገር ውስጥ ዘልላ ትገባለች? የዴሪክ ዊሊያምስ ሞት በራሱ እንዴት ማስጠንቀቂያ
ሊሆናት አልቻለም እያለ በውስጡ ይቃጠል ጀመር፡፡
ኒኪ ቆንጆ እና ብልህ ሴት ልትሆን ትችል ይሆናል፤ ነገር ግን ራሷን ልትወጣበት ከማትችለው ጥልቅ ውሃ ውስጥ ነው የተከተተችው፡፡ የውሃውን ጥልቀት ደግሞ በደንብ የሚያውቀው ጉድማን ነው::....
✨ይቀጥላል✨
👍1
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
...«አይዞሽ አትፍሪ! እዚህ እኔ አልጋ ላይ ወጥተሽ ተኚ፡ ስንገባ ማንም አላየ» ብዬ እየተርበተበትኩ በሩን ዘግቼባት ውልቅ አልኩ፡፡
በድንኳኑና በምድረ ግቢው ውስጥ ግማሽ ሰዓት ያህል ከተዘዋወርኩ በኋላ
አንዳች አካላዊ ኃይል እየገፈትረና እያፍነከነከ ወደ መኝታ ቤቴ ወሰደኝ፡፡ ሰውነቷ በሥራ ድካም በመቀጥቀጡ አንቀላፍታ ስለ ነበር ከደረቷ በላይ ገልጬ አየኋት:: ዘና ብላ በጀርባዋ በመተኛቷ እንቅስቃሴው የሰከነ ውበት ረቦባታል።
የአካላቴን ኃይለኛ ሰደድ ለመቀነስ የተከደኑ ዐይኖችዋን እና የተገጠሙ
ከንፈሮቿን ዳበስኳቸው:: በወዲያነሽ ልብ ውስጥ ልዩ የሆነ የመኖሪያ ዓለም
አሰስኩ።
አንድ ራሴን ለመቆጣጠርና ለመግታት ያልቻልኩበት የነዳድና የአካላዊ
ውጥረት ቅፅበት ደረሰ፡፡ በስተራስጌ በኩል አልጋው ጫፍ ላይ ዐረፍ ስል ነቃች።
ዐይኖቿ በፍቅር ቦግታ ልባዊ መስተንግዶ አደረጉልኝ፡፡ ወዲያው ፊቷን አዙሪ ሆድና ጉልበቷን አጣብቃ በፍርሃት እየተንቀረቀበች ተኛች፡፡ ከጎኗ ጋደም
አልኩ፡፡
ከገላዋ ላይ በወጣው ሙቀት ለብ ያለው የብርድ ልብስ ውስጥ ኣየር የሚያፍነከንክ ደስታ ሰጠኝ፡፡ ልብሷን በሙሉ አወላልቃ በመተኛቷ ገራገርነቷ ከፍላጎቴ ኃይል ጋር ትንቅንቅ ገጠመ፡፡
አንድ ኃይለኛ የሥጋዊ ፍላጎት ግፊት ናጠኝ። ራስን በመግታት ለፍላጐት በመንበርከክ መካከል የቀበጠ ፍልሚያ ተፈጠረ፡፡ የየወዲያነሽ ሕይወት
በእኔ ግድየለሽነት የሚሰናከል መሰለኝ፡፡
«ፍላጐቴን ፈጽሜ ስሜቴን ካረካሁ በኋላ የወዲ ያነሽን እስከ ዘለቄታው
ለመርዳትና በፍቅር ፀንቼ አብሬያት ለመኖር ያለኝ ቆራጥነትና የሕሊና ጥንካሬ
እስከ ምን ድረስ ነው?» እያልኩ በማውጣትና በማውረድ ከራሴ ጋር ትግል ጀምርኩ፡፡ ከራሴ ጋር የማደርገውን ክርክር ሳልደመድምና ኃላፊነቱን ለመሸከም ሳልወስን፡ የየወዲያነሽንም የሕይወትና የኑሮ ሁኔታ አንድ አቅጣጫ እስይዤ ሳልወስን ዕቅፌ አባበልኳት፡፡
ተመሳሳይ ፍላጎቶች ይዋሐዳሉ ሆነና ሰምና ወርቅ ሆንን፡ የልቧ ምት አየለ። የአተነፋፈሷ ፍጥነት በውስጧ ከፍተኛ የስሜት ሲቃ እንዳለ እወጣጡ
ይገልጻል። ለአጭር ጊዜ ትንፋሿን ዋጠች፡፡ ድንገት በመኻሉ የልቅሶ ድምፅ
ሰማሁ፡፡
«ወይኔ እናቴ! ምነው ያንቺን ቀን በሰጠኝ፡፡ ወይኔ ዕድሌ ወይ አለመታደሌ” ብላ ያመቀችውን ትኩስ አየር ለቀቀችው:: እንባዋ እንደ ጎርፍ ይወርድ ጀመር፡፡ በረጂሙ ከተነፈሰች በኋላ ወይኔ ዛሬ ፡ አዬ መከራዪ አዬዬ አበሳዬ!» ብላ በግንባሯ ተደፋች፡፡ ቀጣዮቹ ደቂቃዎች ምን ሊገጥማት እንደሚችል ወለል ብሎ ታይቷታል፡፡ ምንም እንኳ ለቅሶዋና የሚንስፈሰፈው ሰውነቷ ርኅራኄ ቢያሳድሩብኝም አካላዊ ፍላጎቴን ጎትተው የሕሊና ገደብ ሊገድቡብኝ አልቻሉም፡፡ የስሜቴ ልጓም ተበጠሰ፡፡ የልመናዋን መንደርደሪያ ቃላት ከመጤፍ አልቆጠርኳቸውም፡፡
“ይህ ሁሉ ልቅሶና ልመና ይከዳኛል ብለሽ ይሆን? ቃል እገባልሻለሁ አልከዳሽም፡፡ ምንም ቢባል ምንም ቢመጣ እስከመቼም ቢሆን አልከዳሽም፡ ይህ
ፍቅራችን ምስክሬ ነው » ብዬ ደንበኛ የልብ ማጥመጃ ቃል ገባሁ፡፡
ከዚያ በኋላ ቦርቧራ ልቧንና ንጹሕ ልቦናን በአንደበቴ ተጫንኳቸው:: ከግማሽ ሰዓት በኋላ የድንግልናዋን ኪላ ጣስኩት፡፡ እዩዩዋ አንጎሌ ውስጥ ሠረፀ።በመኻሉ የወዲያነሽ እኔ በምሰማው ሁኔታ ብቻ ኡኡ ልትል ስትል አፏን በአፌ ከደንኩት፡፡ ሕሊናዋን ስታ ዧ ብላ ተዘረረች፡፡ ተዝለፈለፈች፡፡ ልቤ በርህራሄና በሀዘኔታ ተንፈራፈረች፡፡
ከአልጋው ላይ ዘልዬ ወረድኩና የተቻለኝን ያህል ረዳኋት፡፡ የሌሊቱን ቀዝቃዛ አየር አርገበገብኩላት፡፡ ድካሟን አቃልዩ ብርታት ልሰጣት ባለመቻሌ በንዴት ተከንኩ። ያም ሆነ ይህ አንዴ ለተፈጸመ ነገር ሌላ አዲስ ፈጻሚ የለውምና እንደገና መብራቱን አጥፍቼ ከጐኗ ጋደም አልኩ። በደረቷ ተደፍታ ለጥ አለች፡፡
ከእንቅልፌ ስነቃ ከሌለቱ ዐሥር ሰዓት ነበር፡፡ በደማቁ የመብራት ብርሃን
በጥቃት የፈዘዘ ውበቷን አየሁት። መኝታችን ተበክሏል። የየወዲያሽ ማራኪ
ዐይኖች ትንገርበዋል፡፡ መብራቱን አጥፍቼ እንደገና ጋደም አልኩ፡፡ ሕልም መሰል
ቅዠቶች እየረከረኩኝ አለፉ፡፡ ዳግመኛ ስነቃ ዐሥራ አንድ ሰዓት ከሃያ ነበር፡፡
የጭንቀትና የፍርሃት ናዳዎች አንጎሌ ውስጥ እየጓኑና እየተውዘገዘጉ ሰላም
አሳጡኝ፡፡ ልብሴን ለበስኩ፡፡ የመኝታ ክፍሌን መስኮት ከፍቼ አሻግሬ ማየት
ጀመርኩ፡፡
የማለዳዋ ፀሐይ ልትወጣ ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ ቀርተዋል፡፡ ከሩቅ
የሚታየው ምሥጢራዊ አድማስ ያልያዘ ግሽርጥ መስሏA። ጎህ ቀደደ። ሰማዩ
በብርሃን አውታሮች ተሽነሸነ፡፡ ጋቢዬን ደርቤና የመስኮቱን ደፍ ተደግፋ የምድረ
ግቢውን የጨለማና የንጋት ውጋት የመጨረሻ ግፊትና የተተከለውን ድንኳን
በዐይነ ችላ አየሁት። ወገገ፡፡ የማለዳው ቀዝቃዛ አየር አካባቢውን በዝግታ ሲያስስ
የእኔም አንጐል በልዩ ልዩ ሐሳብ ተፈተሽ፡፡
የድግሱ አሳላፊዎችና አስተናባሪዎች እንዲሁም እንግዶች ከመነሣታቸው
በፊት የወዲያነሽ መውጣት ስላለባት አልጋው ጫፍ ላይ ተቀመጥኩ፡፡
ግራ እጄን አሾልኬ ርኅራኄ ባጀበው ሁኔታ አንገትና ደረቷን ዳበስኩ:: እውነትም ጥሩ መላ ኖሮ ሳትደነግጥ ነቃች፡፡ ገለጥ ስትል ዐይን ለዐይን በመጋጨታችን ዐይኖቿ በኃፍረት ተሰበሩና ተሸፋፈነች፡፡
የተፈጸመው ሁሉ መታየትም ሆነ መሰማት ስለሌለበት በስጋት ተቅበጠበጥኩ፡፡ ከወላጆቼ በኩል እጅግ ከፍ ያለ የውርደትና የቅሌት ዶፍ
ቃላት እንደሚደርስብኝ ዐውቃለሁ፡፡ እሷም ባልታሰበ የመከራ ውርጂብኝ
እንዳትጐዳ በማሰብ «እስኪ እንደ ምንም ብለሽ ቀና በዪና ተነሽ» ብዩ ትሕትና
ባልተለየው አኳኋት ጠየቅኋት።
ፈገግ ብላ ቀና ስትል ልቤ በደስታ ተለጠጠች፡፡ የደቂቃዎቹ መደራረብና
መተካካት ሙሉ ንጋትን አስከተለ። የአፍንጫዋን ጫፍ በጣቴ እያነቃነቅሁ ከእኔ ጋር ተኝተሽ ማደርሽ እንዳይታወቅና እንዳይሰማ ሰው ሁሉ አንዳንድ እያለ
ከመነሣቱ በፊት ሹልክ ብለሽ ሒጂ» ብዩ ግዴታ የተቀላቀለበትን ንግግሬን
አሰማኋት። ምንም እንኳ ተኝታ ለማርፈድ እንደማትችል ብታውቅም ለጊዜው
ፊቷ በኃዘን ቅጭም አለ። ዐይኖቿ ቀዘዙ፡፡ የሐሳብ ጋሬጣ ጠቀጠቃት፡፡ ልብሷን
ለባብሳና ጸጉሯን እንደ ነገሩ ጎንጉና ከፊት ለፊቴ ቆመች፡፡ ሥቃይዋ አንጀቴን
አላወሰው:: እንደ ሰረቀ ሰው ተሸሽጋ እና ሹክክ ብላ ማንም ሳያይና ሳይሰማ
ወጥታ ሔደች፡፡ ያደረግሁት ድርጊት አስጸያፊና የግድ የለሽነት አሠቃቂ
ተግባር እንደሆነ ገባኝ፡፡ በፍቅር ስም የተፈፀመ ወንጀል፡፡ የእኔ ነገር ግመል ሠርቆ አጎንብሶ ሆነ፡፡ ሆኖም ግብ የለሽ ጸጸት ከተቃወሰ ሕሊና የሚፈልቅ የልቦና እድፍ በመሆኑ በብስጭት ታጥቦ አይጠራምና ድርጊቴ ክፉ አፉን እንደ ከፈተ ቀረ።
ራሴን ከሐሳብ ወጥመድ ነፃ ሳላወጣ፣ ከግራም ከቀኝም ከደጅም ከቤትም
የሰው ድምፅ ተስማ። አንድ ሰዓት ተኩል ላይ ከሰው ጋር ተደባለቅሁ፡፡ ወዲያ
ወዲህ አላልኩም፡፡ ከመኝታ ቤቴ ፊት ለፊት እንግዳ መቀበያው ክፍል ውስጥ
ጉብ አልኩ፡፡
በየወዲያነሽ ልብ ውስጥ አንጸባራቂ እምነት በማስቀመጤ ትነግርብኝ ይሆን? ጉዴን ፀሐይ ታሞቀው ይሆን? በማለት እምብዛም አልሠጋሁ። የውብነሽ
ያደረ ፊቷን ውሃ እንኳ ሳታስነካ ተፍተፍ ስትል መጥታ ያንን የእኔን እረንጓዴ
ፎጣ አንተ መኝታ ቤት ውስጥ አይቼው ነበር» ብላ ብሩን ከፍታ ዘው አለች።
ሰውነቴ የጥቅምት ውርጭ እንዳደረበት ብረት በድንጋጤ ቀዘቀዘ፡፡ ተነሥቼ ለመሸሽ ትንሽ ነበር የቀረኝ ዐይኔ በድንጋጤ ፈጥጦ አፌ ከመቅፅበት ኩበት ሆነ።ድንገት ከጭንቀቴ ምጥ ተገላገልኩ ፎጣውን አንጠልጥላ ተመለሰች፡፡ ልክ እንደ ሰከረ
፡
፡
#ክፍል_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
...«አይዞሽ አትፍሪ! እዚህ እኔ አልጋ ላይ ወጥተሽ ተኚ፡ ስንገባ ማንም አላየ» ብዬ እየተርበተበትኩ በሩን ዘግቼባት ውልቅ አልኩ፡፡
በድንኳኑና በምድረ ግቢው ውስጥ ግማሽ ሰዓት ያህል ከተዘዋወርኩ በኋላ
አንዳች አካላዊ ኃይል እየገፈትረና እያፍነከነከ ወደ መኝታ ቤቴ ወሰደኝ፡፡ ሰውነቷ በሥራ ድካም በመቀጥቀጡ አንቀላፍታ ስለ ነበር ከደረቷ በላይ ገልጬ አየኋት:: ዘና ብላ በጀርባዋ በመተኛቷ እንቅስቃሴው የሰከነ ውበት ረቦባታል።
የአካላቴን ኃይለኛ ሰደድ ለመቀነስ የተከደኑ ዐይኖችዋን እና የተገጠሙ
ከንፈሮቿን ዳበስኳቸው:: በወዲያነሽ ልብ ውስጥ ልዩ የሆነ የመኖሪያ ዓለም
አሰስኩ።
አንድ ራሴን ለመቆጣጠርና ለመግታት ያልቻልኩበት የነዳድና የአካላዊ
ውጥረት ቅፅበት ደረሰ፡፡ በስተራስጌ በኩል አልጋው ጫፍ ላይ ዐረፍ ስል ነቃች።
ዐይኖቿ በፍቅር ቦግታ ልባዊ መስተንግዶ አደረጉልኝ፡፡ ወዲያው ፊቷን አዙሪ ሆድና ጉልበቷን አጣብቃ በፍርሃት እየተንቀረቀበች ተኛች፡፡ ከጎኗ ጋደም
አልኩ፡፡
ከገላዋ ላይ በወጣው ሙቀት ለብ ያለው የብርድ ልብስ ውስጥ ኣየር የሚያፍነከንክ ደስታ ሰጠኝ፡፡ ልብሷን በሙሉ አወላልቃ በመተኛቷ ገራገርነቷ ከፍላጎቴ ኃይል ጋር ትንቅንቅ ገጠመ፡፡
አንድ ኃይለኛ የሥጋዊ ፍላጎት ግፊት ናጠኝ። ራስን በመግታት ለፍላጐት በመንበርከክ መካከል የቀበጠ ፍልሚያ ተፈጠረ፡፡ የየወዲያነሽ ሕይወት
በእኔ ግድየለሽነት የሚሰናከል መሰለኝ፡፡
«ፍላጐቴን ፈጽሜ ስሜቴን ካረካሁ በኋላ የወዲ ያነሽን እስከ ዘለቄታው
ለመርዳትና በፍቅር ፀንቼ አብሬያት ለመኖር ያለኝ ቆራጥነትና የሕሊና ጥንካሬ
እስከ ምን ድረስ ነው?» እያልኩ በማውጣትና በማውረድ ከራሴ ጋር ትግል ጀምርኩ፡፡ ከራሴ ጋር የማደርገውን ክርክር ሳልደመድምና ኃላፊነቱን ለመሸከም ሳልወስን፡ የየወዲያነሽንም የሕይወትና የኑሮ ሁኔታ አንድ አቅጣጫ እስይዤ ሳልወስን ዕቅፌ አባበልኳት፡፡
ተመሳሳይ ፍላጎቶች ይዋሐዳሉ ሆነና ሰምና ወርቅ ሆንን፡ የልቧ ምት አየለ። የአተነፋፈሷ ፍጥነት በውስጧ ከፍተኛ የስሜት ሲቃ እንዳለ እወጣጡ
ይገልጻል። ለአጭር ጊዜ ትንፋሿን ዋጠች፡፡ ድንገት በመኻሉ የልቅሶ ድምፅ
ሰማሁ፡፡
«ወይኔ እናቴ! ምነው ያንቺን ቀን በሰጠኝ፡፡ ወይኔ ዕድሌ ወይ አለመታደሌ” ብላ ያመቀችውን ትኩስ አየር ለቀቀችው:: እንባዋ እንደ ጎርፍ ይወርድ ጀመር፡፡ በረጂሙ ከተነፈሰች በኋላ ወይኔ ዛሬ ፡ አዬ መከራዪ አዬዬ አበሳዬ!» ብላ በግንባሯ ተደፋች፡፡ ቀጣዮቹ ደቂቃዎች ምን ሊገጥማት እንደሚችል ወለል ብሎ ታይቷታል፡፡ ምንም እንኳ ለቅሶዋና የሚንስፈሰፈው ሰውነቷ ርኅራኄ ቢያሳድሩብኝም አካላዊ ፍላጎቴን ጎትተው የሕሊና ገደብ ሊገድቡብኝ አልቻሉም፡፡ የስሜቴ ልጓም ተበጠሰ፡፡ የልመናዋን መንደርደሪያ ቃላት ከመጤፍ አልቆጠርኳቸውም፡፡
“ይህ ሁሉ ልቅሶና ልመና ይከዳኛል ብለሽ ይሆን? ቃል እገባልሻለሁ አልከዳሽም፡፡ ምንም ቢባል ምንም ቢመጣ እስከመቼም ቢሆን አልከዳሽም፡ ይህ
ፍቅራችን ምስክሬ ነው » ብዬ ደንበኛ የልብ ማጥመጃ ቃል ገባሁ፡፡
ከዚያ በኋላ ቦርቧራ ልቧንና ንጹሕ ልቦናን በአንደበቴ ተጫንኳቸው:: ከግማሽ ሰዓት በኋላ የድንግልናዋን ኪላ ጣስኩት፡፡ እዩዩዋ አንጎሌ ውስጥ ሠረፀ።በመኻሉ የወዲያነሽ እኔ በምሰማው ሁኔታ ብቻ ኡኡ ልትል ስትል አፏን በአፌ ከደንኩት፡፡ ሕሊናዋን ስታ ዧ ብላ ተዘረረች፡፡ ተዝለፈለፈች፡፡ ልቤ በርህራሄና በሀዘኔታ ተንፈራፈረች፡፡
ከአልጋው ላይ ዘልዬ ወረድኩና የተቻለኝን ያህል ረዳኋት፡፡ የሌሊቱን ቀዝቃዛ አየር አርገበገብኩላት፡፡ ድካሟን አቃልዩ ብርታት ልሰጣት ባለመቻሌ በንዴት ተከንኩ። ያም ሆነ ይህ አንዴ ለተፈጸመ ነገር ሌላ አዲስ ፈጻሚ የለውምና እንደገና መብራቱን አጥፍቼ ከጐኗ ጋደም አልኩ። በደረቷ ተደፍታ ለጥ አለች፡፡
ከእንቅልፌ ስነቃ ከሌለቱ ዐሥር ሰዓት ነበር፡፡ በደማቁ የመብራት ብርሃን
በጥቃት የፈዘዘ ውበቷን አየሁት። መኝታችን ተበክሏል። የየወዲያሽ ማራኪ
ዐይኖች ትንገርበዋል፡፡ መብራቱን አጥፍቼ እንደገና ጋደም አልኩ፡፡ ሕልም መሰል
ቅዠቶች እየረከረኩኝ አለፉ፡፡ ዳግመኛ ስነቃ ዐሥራ አንድ ሰዓት ከሃያ ነበር፡፡
የጭንቀትና የፍርሃት ናዳዎች አንጎሌ ውስጥ እየጓኑና እየተውዘገዘጉ ሰላም
አሳጡኝ፡፡ ልብሴን ለበስኩ፡፡ የመኝታ ክፍሌን መስኮት ከፍቼ አሻግሬ ማየት
ጀመርኩ፡፡
የማለዳዋ ፀሐይ ልትወጣ ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ ቀርተዋል፡፡ ከሩቅ
የሚታየው ምሥጢራዊ አድማስ ያልያዘ ግሽርጥ መስሏA። ጎህ ቀደደ። ሰማዩ
በብርሃን አውታሮች ተሽነሸነ፡፡ ጋቢዬን ደርቤና የመስኮቱን ደፍ ተደግፋ የምድረ
ግቢውን የጨለማና የንጋት ውጋት የመጨረሻ ግፊትና የተተከለውን ድንኳን
በዐይነ ችላ አየሁት። ወገገ፡፡ የማለዳው ቀዝቃዛ አየር አካባቢውን በዝግታ ሲያስስ
የእኔም አንጐል በልዩ ልዩ ሐሳብ ተፈተሽ፡፡
የድግሱ አሳላፊዎችና አስተናባሪዎች እንዲሁም እንግዶች ከመነሣታቸው
በፊት የወዲያነሽ መውጣት ስላለባት አልጋው ጫፍ ላይ ተቀመጥኩ፡፡
ግራ እጄን አሾልኬ ርኅራኄ ባጀበው ሁኔታ አንገትና ደረቷን ዳበስኩ:: እውነትም ጥሩ መላ ኖሮ ሳትደነግጥ ነቃች፡፡ ገለጥ ስትል ዐይን ለዐይን በመጋጨታችን ዐይኖቿ በኃፍረት ተሰበሩና ተሸፋፈነች፡፡
የተፈጸመው ሁሉ መታየትም ሆነ መሰማት ስለሌለበት በስጋት ተቅበጠበጥኩ፡፡ ከወላጆቼ በኩል እጅግ ከፍ ያለ የውርደትና የቅሌት ዶፍ
ቃላት እንደሚደርስብኝ ዐውቃለሁ፡፡ እሷም ባልታሰበ የመከራ ውርጂብኝ
እንዳትጐዳ በማሰብ «እስኪ እንደ ምንም ብለሽ ቀና በዪና ተነሽ» ብዩ ትሕትና
ባልተለየው አኳኋት ጠየቅኋት።
ፈገግ ብላ ቀና ስትል ልቤ በደስታ ተለጠጠች፡፡ የደቂቃዎቹ መደራረብና
መተካካት ሙሉ ንጋትን አስከተለ። የአፍንጫዋን ጫፍ በጣቴ እያነቃነቅሁ ከእኔ ጋር ተኝተሽ ማደርሽ እንዳይታወቅና እንዳይሰማ ሰው ሁሉ አንዳንድ እያለ
ከመነሣቱ በፊት ሹልክ ብለሽ ሒጂ» ብዩ ግዴታ የተቀላቀለበትን ንግግሬን
አሰማኋት። ምንም እንኳ ተኝታ ለማርፈድ እንደማትችል ብታውቅም ለጊዜው
ፊቷ በኃዘን ቅጭም አለ። ዐይኖቿ ቀዘዙ፡፡ የሐሳብ ጋሬጣ ጠቀጠቃት፡፡ ልብሷን
ለባብሳና ጸጉሯን እንደ ነገሩ ጎንጉና ከፊት ለፊቴ ቆመች፡፡ ሥቃይዋ አንጀቴን
አላወሰው:: እንደ ሰረቀ ሰው ተሸሽጋ እና ሹክክ ብላ ማንም ሳያይና ሳይሰማ
ወጥታ ሔደች፡፡ ያደረግሁት ድርጊት አስጸያፊና የግድ የለሽነት አሠቃቂ
ተግባር እንደሆነ ገባኝ፡፡ በፍቅር ስም የተፈፀመ ወንጀል፡፡ የእኔ ነገር ግመል ሠርቆ አጎንብሶ ሆነ፡፡ ሆኖም ግብ የለሽ ጸጸት ከተቃወሰ ሕሊና የሚፈልቅ የልቦና እድፍ በመሆኑ በብስጭት ታጥቦ አይጠራምና ድርጊቴ ክፉ አፉን እንደ ከፈተ ቀረ።
ራሴን ከሐሳብ ወጥመድ ነፃ ሳላወጣ፣ ከግራም ከቀኝም ከደጅም ከቤትም
የሰው ድምፅ ተስማ። አንድ ሰዓት ተኩል ላይ ከሰው ጋር ተደባለቅሁ፡፡ ወዲያ
ወዲህ አላልኩም፡፡ ከመኝታ ቤቴ ፊት ለፊት እንግዳ መቀበያው ክፍል ውስጥ
ጉብ አልኩ፡፡
በየወዲያነሽ ልብ ውስጥ አንጸባራቂ እምነት በማስቀመጤ ትነግርብኝ ይሆን? ጉዴን ፀሐይ ታሞቀው ይሆን? በማለት እምብዛም አልሠጋሁ። የውብነሽ
ያደረ ፊቷን ውሃ እንኳ ሳታስነካ ተፍተፍ ስትል መጥታ ያንን የእኔን እረንጓዴ
ፎጣ አንተ መኝታ ቤት ውስጥ አይቼው ነበር» ብላ ብሩን ከፍታ ዘው አለች።
ሰውነቴ የጥቅምት ውርጭ እንዳደረበት ብረት በድንጋጤ ቀዘቀዘ፡፡ ተነሥቼ ለመሸሽ ትንሽ ነበር የቀረኝ ዐይኔ በድንጋጤ ፈጥጦ አፌ ከመቅፅበት ኩበት ሆነ።ድንገት ከጭንቀቴ ምጥ ተገላገልኩ ፎጣውን አንጠልጥላ ተመለሰች፡፡ ልክ እንደ ሰከረ
👍3
ሰው እየተፍገመገምኩ መኝታ ቤቴ ውስጥ ገባሁ፡፡የእኔና የወድያነሽን ድብቅ ድርጋት ግን ያ በሚገባ ያልተነጠፈውና በዘፈቀደ
የተዘረጋው የብርድ ልብስና የአልጋ ልብስ ሽፍነው ሰወሩት።
መጀመሪያውኑ ያለመጠንቀቄና ልብሶቼን ገለል ያለማድረጌ የፈጠረው ስሕተት እንደ ትልቅ ጋራ ተገትሮ ታየኝ። ሁኔታው ባለመጋለጡ የልቤ ምት ቀነሰ፡ ረቂቅ ውስጣዊ እፎይታ አገኘሁ።
እናቴ የቤቱንና የእንግዶቹን ሁኔታ ለመመልከት ከላይ ታች ስትል
እኔም ለወሬ ቃሪማ ተከትያት ምድር ቤት ወረድኩ።
የወዲያነሽ ከአንድ ትልቅ የብረት በርሜል አጠገብ ለደረቆት ማስጫና ለኮቸሮ ማድረቂያ ተብሎ በተገዛ አዲስ ሰሌን ላይ ተኮራምታ ተኝታ አገኘናት። ከሰሌኑ ላይ ቀሚሷን ጣል አድርጋ ነጠላ ብጤ ለብሳለች።
ከአባቴ ጋር አንዳችም ግንኙነት እንደሌላት በመረጋገጡ የእናቴ ጥርጣሬ
ተወግዷል። የወዲያነሽን በጣም ስለ ወደደቻትና በሥራዋም አንጀቷ በራሱ
ወዲያው እንዳየቻት «ውይ! ዐፈር በበላሁት! ይቺን ልጅ ምን ነካብኝ?» ብላ
አጎነበሰች፡፡ «እቴ እመመሽ እንዴ?» ብላ ርኅራኄዋን በሚያስረዳ ለዛማ ድምፅ
ጠየቀቻት። እናቴ «እቴ» ብሎ የመጥራት ልማድ አለባት። የወዲያነሽ ቀና ብላ
ከተቀመጠች በኋላ «ይኸ ራሴ እንደ ድንጋይ ነው የከበደኝ፡ መነሣት አቅቶኝ ነው “ዝም ብዩ የተኛሁት» ብላ ጉልበቷ ላይ በግንባሯ ደፋ ኣለች።
እናቴ እንደገና ከመናገሯ በፊት «ታዲያ ምንስ ቢያምንና መነሣትስ ቢያቅትሽ ከዚህ ከመንገዱ ላይና ከሰው ፊት ዘወር ማለት አቃተሽ እንዴ? ምን ነውር የማትፈራ ናት እባካችሁ?» በማለት አደናጋሪ የውሸት ቁጣ ተቆጣሁ፡፡
እናቴ ወደ እኔ መለስ ብላ «አንተ ምን ችግር አለብህ ልጄ! የሞላለት
ድመት ሳምባ ያማርጣል” ይላሉ መምሬ መታፈሪያ፡፡ «ታዲያ ለጊዜውስ ቢሆን
የት ትተኛ ብለህ ነው? አልጋዋን እንደሆነ ለእንግዳ ሰጠንባት፡፡ እሳቸውም
የትላንቱ ስካር ተጭኗቸው ይኸው እስካሁን ንቅንቅ አላሉም፡፡ ኧረ ምን በወጣት ድሃዋ ! ለእኔስ አይመምብኝ፡፡ እሷው ናት ያለችኝ፡ ግን ከወዲያ ወዲህ ብሎ ሊሠራልኝ?» ብላ ዐይኖቿን ወደ የወዲያነሽ መለሰቻቸው፡፡
እሱስ እውነትሽን ነው» እልኳት ሐሳቧን ከሐሳቤ ጋር ለማገናኘት ያህል። «ግን እንደ አህያ ሬሳ እዚህ ሜዳ ላይ ተፈንችራ ብትታይ ምን ጥቅም አለው?» ብዬ ልቀጥል ስል እናቴ በፀያፉ ንግግሬ ተቆጥታ ክፉኛ ገላመጠችኝ፡፡
እኔም ውስጤ እንደቀለለ ተሰማኝ፡፡ “ማለቴ» ብዬ ነገሬን ለማረቅ ተነሳሁ «ሌላ
ቦታ ሔዳ አንጥፋ ትተኛ ወይም ለጊዜው እኔ መኝታ ቤት ወለሉን ጠርጋ ጋዳም ትበል። ባይሆነ ማታ በደንብ አድረጋ ትወለውለዋለች» ብዬ ስውር ጥቅም
ያንዠረገገ ሐሳብ አቀረብኩ፡፡ እናቴ በሐሳቡ በመስማማቷ፡ የወዲያነሽ ሌላ ንጹሕ ሥጋጃ አንጥፋ እኔ መኝታ ክፍል ውስጥ ተኛች፡፡ በእኔ ስውር ምክንያትና በእናቴ የዋህነት መካካል አንዳች የሚሐል የሐሳብ ልዩነት ነበር ከጥቂት
ደቂቃዎች በኋላ ነገሩን በማረሳሳት ቀስ ብዬ ገብቼ ያን አልፎ አልፎ ጃኖ የመሰለ
አንሶላ ሽምልዩ ሳጥን ውስጥ ቆለፍኩበት፡፡ በምትኩም ሌላ ልብስ እነጣጥፈ ወጣሁ፡፡
ሰው ሁሉ ያደረ ሆዱን ለመሙላት በየመዐዱ ዙሪያ ተኮልኩሎ ስለ ነበር
እኔም «ለእኔ ነው» ብዬ ለየወዲያነሽ ጥሩ ቁርስ ይዤላት ገባሁ።ሽብረክ ብዬ ፊቷን ካየሁ በኋላ «በይ ተነሺና አልጋው ላይ ወጥተሽ ተኚ፡ ማንም ገብቶ እንዳያይሽ በሩን ቆልፌብሽ እሔዳለሁ፡፡ ቅድም በእናቴ ፊት የተቆጣሁሽና የጮሁኩብሽ ዐውቄ ነው:: እንዲያ ባልቆጣና ይህን ብልሃት ባልጣበብ ኖሮ አንቺን እዚህ ማስገባት አልችልም ነበር፡፡ ማታ ተመልሼ ስመጣና ይህን በር ስከፍት ኣልጋው ላይ መተኛትሽን ሌላ ሰው እንዳያይ ድምፄን ከሩቅ ስትሰሚ ቶሎ ወርደሽ ወለሉ ላይ ተኚ» ብያት ስነሣ ቀና ብላ ተቀመጠች፡፡ ድንገት ሳላስበው ጫማዩ ላይ ዘፍ አለች፡ እድራጎቷ ከመጠን በላይ ዘገነነኝ። ሆኖም ሆነ ! ቀስ ብዪ አልጋው ላይ ካስተኛኋት በኋላ በሩን ከውጭ ቆልፈባት ሔድኩ፡፡
ሊደረግላት የሚገባው ክብካቤ ይህ ባይሆንም በአካሏ ላይ ለደረሰው ጉዳት
ጸጥታማ ዕረፍት እንኳ ታገኝ ዘንድ ሆን ብዬ ወደ ቤት ሳለመለስ ዋልኩ።
ከዐስራ ሁለት ሰዓት በኋላ ወደ ቤት ገባሁ፡፡ ብቻዋን ተዳፍኖባት በመዋሏ
ልባዊ ቅሬታ እንከረደደኝ፡፡ ምንም እንኳ ከአልጋ ወርዳ መሬት ላይ መተኛቷን
ደስ ባልሰኝበትም ጊዜውና ሁኔታው በማስገደዱ እንግዳ መቀበያ ክፍል ውስጥ እንደ ደረስኩ ከእናቴና ከየውብነሽ ጋር ጎላ ባለ ድምዕ ሰላምታ ተለዋወጥኩ። የድምፂ ጉላት የሚጠቅመው ግን እኔን በመጠባበቅ ላይ ለነበረችው ለየወዲያነሽ ነበር፡፡ በሩን ከፍቼ ስገባ እንደተባባልነው ተኝታ አገኘኋት። በየወዲያነሽ አልጋ ላይ ያደሩት ሽማግሌ ሌላ አሮጌ አልጋ ስለ ተሰጣቸው የወዲያነሽ እልጋዋ ላይ ተኛች።
ቀን በቀን ላይ ተደራረበ፡፡ አድራጎታችን ሁሉ ሳይሰማ አያሌ ሳምንታት ዐለፉ፡፡ እያደር ግንኙነታችን እየለማ የፍቅራችን አዝመራ አበበ። የልቦቻችን ብርሃናዊ የፍቅር ገመድ እየጠበቀ ደመቀ፡፡ ከዚያም ምን ጊዜም ቢሆን በሌሎች ሰዎችና በቤተሰቦቼ ፊት አንቱ» ለብቻችን ስንሆን ግን «አንተ» ወይም «ጌታነሀ» ብላ እንድትጠራኝ ተስማማን፡፡ ለተዋሃዱ ተማማኝ ልቦች አዳጋች ነገር የለምና ወዲያው ለመደችው:: ምንኛ ደስ ይላል፡፡
ጊዜው ገሠገሠ፡፡ አንድ ዓመት ከመንፈቋ እንደዘበት ነበር ሆነ። የውብነሽ
እዳዲስ ልብሶች ባስቀደደች ቁጥር አርጀትጀት ያለባትንና ወረቱ ያለቀበትን
ትሰጣት ነበር፡፡ ይህም የሁለቱ መግባባትና መፋቀር በእናቴና በየወዲያነሽ መካከል የነበረውን ተራ ግንኙነት ኮላው።
የየወዲያነሽ ሕይወትና ኑሮ ሌላው የሕይወቴ ገጽታ በመሆኑ ዕለታዊ
ብስጭቷና የኑሮዋ ሽክረት ይቆረቁረኛል። ከትምህርት ቤትና ከዚያም ውጭ
ጥቂት ሴቶች ዐውቅ ነበር፡፡ ዐልፎ ዐልፎም አንድና ሁለቱን የወደድኩበት ጊዜ ነበር።
የወዲያነሽን ካፈቀርኩ በኋላ ግን አኳኋኔ ሁሉ ከቀድሞው የተለየ ሆነ፡፡ ስለ ቀድሞዎቹ የነበረኝ ስሜት ሁሉ ተራ ትዝታ ሆነ፡፡ ያጋጣሚ ጉዳይ ሆኖ ያጋጠሙኝ ሴቶች ወረተኞች ስለ ነበሩ ግንኙነታችን ሁሉ ውሎ ሲያድር የተቀጠፈ አበባ ውበት ሆኖ ቀረ። ይህም በመሆኑ ስሜቴ ተገማሽሮ የፍቅርን ልዩ ለዛ ያሞገስኩበት ቀን አይታወሰኝም፡፡
ከየወዲያነሽ ጋር ያለኝ ምዑዝ ፍቅር ግን ልዩና ጠንካራ በመሆኑ ሌሎቹን ሁሉ ደመሰሳቸው:: የእርሷም በቤታችን ውስጥ ሠራተኛ መሆን ቅንጣት ታህል ቅር አላሠኘኝም፡፡
አንዳንድ ጊዜ ያቺ በውስጤ የምትፍለከለከዋ ጤዛ የምታህል ወኔዬ
ድንገት በምትገነፍልበት ጊዜ «ከዛሬ ጀምሮ ከትክክለኛ አመለካከት ውጭ
የሆነውን አስተሳሰብ ለመቋቋምና ለመበረቃቀስ ቆራጩ እነሣለሁ፡፡ በወዲያነሽ የተነሣ ምንም ዐይነት መጥፎ ሁኔታና አደጋ ቢደርስብኝ ግንባሬን አላጥፍም፡፡
«ከእንግዲህ ወዲያ የትልቅ ሰው ልጅ አጥንተ ጥሩ እና ደመ ንጹሕ
በሚለው ከንቱ አሮጌ እምነት በጭራሽ አላምንም፡፡ በእኔና በእርሷ መካከል የኑሮ
ደረጃ፣ ሀብታምና ድሃ ሆኖ የመወለድ ልዩነት እንጂ በተፈጥሮ ሰዉነት መበላለጥ ስለ ሌለ እስከ ዘለቄታው ከእርሷ ጋር መኖር እችላለሁ፡፡
«የአስተሳሰባችን ያለ መቀራረብ የሚያስከትለውም ችግር እንዲወገድ
የጋራ ጥረት ማድረግ ይቻላል፡፡ እኔና እርሷ በሰውነታችን ፍፁም እኩል መሆናችንን እኔዉ ለእኔ ማረጋገጥና ማሳወቅ ይኖርብኛል» እያልኩ በሐሳብ ሽቅብ
እመጥቅና እንደገና ደግሞ ቁልቁል ወርጄ ዘጭ እላለሁ፡፡ በሐሳብ ሠረገላ ላይ
ተቀምጩ የሐሳብ ልጓም ስስብና ስለቅ አያሌ ቀናት ዐለፉ፡፡
እናቴ ከራት በኋላ የተፈላውን ቡና እንዳከተመች ከተቀመጠችበት
ትንቡኬ ወንበር ላይ በዝግታ ተነሥታ ከደረቷ
የተዘረጋው የብርድ ልብስና የአልጋ ልብስ ሽፍነው ሰወሩት።
መጀመሪያውኑ ያለመጠንቀቄና ልብሶቼን ገለል ያለማድረጌ የፈጠረው ስሕተት እንደ ትልቅ ጋራ ተገትሮ ታየኝ። ሁኔታው ባለመጋለጡ የልቤ ምት ቀነሰ፡ ረቂቅ ውስጣዊ እፎይታ አገኘሁ።
እናቴ የቤቱንና የእንግዶቹን ሁኔታ ለመመልከት ከላይ ታች ስትል
እኔም ለወሬ ቃሪማ ተከትያት ምድር ቤት ወረድኩ።
የወዲያነሽ ከአንድ ትልቅ የብረት በርሜል አጠገብ ለደረቆት ማስጫና ለኮቸሮ ማድረቂያ ተብሎ በተገዛ አዲስ ሰሌን ላይ ተኮራምታ ተኝታ አገኘናት። ከሰሌኑ ላይ ቀሚሷን ጣል አድርጋ ነጠላ ብጤ ለብሳለች።
ከአባቴ ጋር አንዳችም ግንኙነት እንደሌላት በመረጋገጡ የእናቴ ጥርጣሬ
ተወግዷል። የወዲያነሽን በጣም ስለ ወደደቻትና በሥራዋም አንጀቷ በራሱ
ወዲያው እንዳየቻት «ውይ! ዐፈር በበላሁት! ይቺን ልጅ ምን ነካብኝ?» ብላ
አጎነበሰች፡፡ «እቴ እመመሽ እንዴ?» ብላ ርኅራኄዋን በሚያስረዳ ለዛማ ድምፅ
ጠየቀቻት። እናቴ «እቴ» ብሎ የመጥራት ልማድ አለባት። የወዲያነሽ ቀና ብላ
ከተቀመጠች በኋላ «ይኸ ራሴ እንደ ድንጋይ ነው የከበደኝ፡ መነሣት አቅቶኝ ነው “ዝም ብዩ የተኛሁት» ብላ ጉልበቷ ላይ በግንባሯ ደፋ ኣለች።
እናቴ እንደገና ከመናገሯ በፊት «ታዲያ ምንስ ቢያምንና መነሣትስ ቢያቅትሽ ከዚህ ከመንገዱ ላይና ከሰው ፊት ዘወር ማለት አቃተሽ እንዴ? ምን ነውር የማትፈራ ናት እባካችሁ?» በማለት አደናጋሪ የውሸት ቁጣ ተቆጣሁ፡፡
እናቴ ወደ እኔ መለስ ብላ «አንተ ምን ችግር አለብህ ልጄ! የሞላለት
ድመት ሳምባ ያማርጣል” ይላሉ መምሬ መታፈሪያ፡፡ «ታዲያ ለጊዜውስ ቢሆን
የት ትተኛ ብለህ ነው? አልጋዋን እንደሆነ ለእንግዳ ሰጠንባት፡፡ እሳቸውም
የትላንቱ ስካር ተጭኗቸው ይኸው እስካሁን ንቅንቅ አላሉም፡፡ ኧረ ምን በወጣት ድሃዋ ! ለእኔስ አይመምብኝ፡፡ እሷው ናት ያለችኝ፡ ግን ከወዲያ ወዲህ ብሎ ሊሠራልኝ?» ብላ ዐይኖቿን ወደ የወዲያነሽ መለሰቻቸው፡፡
እሱስ እውነትሽን ነው» እልኳት ሐሳቧን ከሐሳቤ ጋር ለማገናኘት ያህል። «ግን እንደ አህያ ሬሳ እዚህ ሜዳ ላይ ተፈንችራ ብትታይ ምን ጥቅም አለው?» ብዬ ልቀጥል ስል እናቴ በፀያፉ ንግግሬ ተቆጥታ ክፉኛ ገላመጠችኝ፡፡
እኔም ውስጤ እንደቀለለ ተሰማኝ፡፡ “ማለቴ» ብዬ ነገሬን ለማረቅ ተነሳሁ «ሌላ
ቦታ ሔዳ አንጥፋ ትተኛ ወይም ለጊዜው እኔ መኝታ ቤት ወለሉን ጠርጋ ጋዳም ትበል። ባይሆነ ማታ በደንብ አድረጋ ትወለውለዋለች» ብዬ ስውር ጥቅም
ያንዠረገገ ሐሳብ አቀረብኩ፡፡ እናቴ በሐሳቡ በመስማማቷ፡ የወዲያነሽ ሌላ ንጹሕ ሥጋጃ አንጥፋ እኔ መኝታ ክፍል ውስጥ ተኛች፡፡ በእኔ ስውር ምክንያትና በእናቴ የዋህነት መካካል አንዳች የሚሐል የሐሳብ ልዩነት ነበር ከጥቂት
ደቂቃዎች በኋላ ነገሩን በማረሳሳት ቀስ ብዬ ገብቼ ያን አልፎ አልፎ ጃኖ የመሰለ
አንሶላ ሽምልዩ ሳጥን ውስጥ ቆለፍኩበት፡፡ በምትኩም ሌላ ልብስ እነጣጥፈ ወጣሁ፡፡
ሰው ሁሉ ያደረ ሆዱን ለመሙላት በየመዐዱ ዙሪያ ተኮልኩሎ ስለ ነበር
እኔም «ለእኔ ነው» ብዬ ለየወዲያነሽ ጥሩ ቁርስ ይዤላት ገባሁ።ሽብረክ ብዬ ፊቷን ካየሁ በኋላ «በይ ተነሺና አልጋው ላይ ወጥተሽ ተኚ፡ ማንም ገብቶ እንዳያይሽ በሩን ቆልፌብሽ እሔዳለሁ፡፡ ቅድም በእናቴ ፊት የተቆጣሁሽና የጮሁኩብሽ ዐውቄ ነው:: እንዲያ ባልቆጣና ይህን ብልሃት ባልጣበብ ኖሮ አንቺን እዚህ ማስገባት አልችልም ነበር፡፡ ማታ ተመልሼ ስመጣና ይህን በር ስከፍት ኣልጋው ላይ መተኛትሽን ሌላ ሰው እንዳያይ ድምፄን ከሩቅ ስትሰሚ ቶሎ ወርደሽ ወለሉ ላይ ተኚ» ብያት ስነሣ ቀና ብላ ተቀመጠች፡፡ ድንገት ሳላስበው ጫማዩ ላይ ዘፍ አለች፡ እድራጎቷ ከመጠን በላይ ዘገነነኝ። ሆኖም ሆነ ! ቀስ ብዪ አልጋው ላይ ካስተኛኋት በኋላ በሩን ከውጭ ቆልፈባት ሔድኩ፡፡
ሊደረግላት የሚገባው ክብካቤ ይህ ባይሆንም በአካሏ ላይ ለደረሰው ጉዳት
ጸጥታማ ዕረፍት እንኳ ታገኝ ዘንድ ሆን ብዬ ወደ ቤት ሳለመለስ ዋልኩ።
ከዐስራ ሁለት ሰዓት በኋላ ወደ ቤት ገባሁ፡፡ ብቻዋን ተዳፍኖባት በመዋሏ
ልባዊ ቅሬታ እንከረደደኝ፡፡ ምንም እንኳ ከአልጋ ወርዳ መሬት ላይ መተኛቷን
ደስ ባልሰኝበትም ጊዜውና ሁኔታው በማስገደዱ እንግዳ መቀበያ ክፍል ውስጥ እንደ ደረስኩ ከእናቴና ከየውብነሽ ጋር ጎላ ባለ ድምዕ ሰላምታ ተለዋወጥኩ። የድምፂ ጉላት የሚጠቅመው ግን እኔን በመጠባበቅ ላይ ለነበረችው ለየወዲያነሽ ነበር፡፡ በሩን ከፍቼ ስገባ እንደተባባልነው ተኝታ አገኘኋት። በየወዲያነሽ አልጋ ላይ ያደሩት ሽማግሌ ሌላ አሮጌ አልጋ ስለ ተሰጣቸው የወዲያነሽ እልጋዋ ላይ ተኛች።
ቀን በቀን ላይ ተደራረበ፡፡ አድራጎታችን ሁሉ ሳይሰማ አያሌ ሳምንታት ዐለፉ፡፡ እያደር ግንኙነታችን እየለማ የፍቅራችን አዝመራ አበበ። የልቦቻችን ብርሃናዊ የፍቅር ገመድ እየጠበቀ ደመቀ፡፡ ከዚያም ምን ጊዜም ቢሆን በሌሎች ሰዎችና በቤተሰቦቼ ፊት አንቱ» ለብቻችን ስንሆን ግን «አንተ» ወይም «ጌታነሀ» ብላ እንድትጠራኝ ተስማማን፡፡ ለተዋሃዱ ተማማኝ ልቦች አዳጋች ነገር የለምና ወዲያው ለመደችው:: ምንኛ ደስ ይላል፡፡
ጊዜው ገሠገሠ፡፡ አንድ ዓመት ከመንፈቋ እንደዘበት ነበር ሆነ። የውብነሽ
እዳዲስ ልብሶች ባስቀደደች ቁጥር አርጀትጀት ያለባትንና ወረቱ ያለቀበትን
ትሰጣት ነበር፡፡ ይህም የሁለቱ መግባባትና መፋቀር በእናቴና በየወዲያነሽ መካከል የነበረውን ተራ ግንኙነት ኮላው።
የየወዲያነሽ ሕይወትና ኑሮ ሌላው የሕይወቴ ገጽታ በመሆኑ ዕለታዊ
ብስጭቷና የኑሮዋ ሽክረት ይቆረቁረኛል። ከትምህርት ቤትና ከዚያም ውጭ
ጥቂት ሴቶች ዐውቅ ነበር፡፡ ዐልፎ ዐልፎም አንድና ሁለቱን የወደድኩበት ጊዜ ነበር።
የወዲያነሽን ካፈቀርኩ በኋላ ግን አኳኋኔ ሁሉ ከቀድሞው የተለየ ሆነ፡፡ ስለ ቀድሞዎቹ የነበረኝ ስሜት ሁሉ ተራ ትዝታ ሆነ፡፡ ያጋጣሚ ጉዳይ ሆኖ ያጋጠሙኝ ሴቶች ወረተኞች ስለ ነበሩ ግንኙነታችን ሁሉ ውሎ ሲያድር የተቀጠፈ አበባ ውበት ሆኖ ቀረ። ይህም በመሆኑ ስሜቴ ተገማሽሮ የፍቅርን ልዩ ለዛ ያሞገስኩበት ቀን አይታወሰኝም፡፡
ከየወዲያነሽ ጋር ያለኝ ምዑዝ ፍቅር ግን ልዩና ጠንካራ በመሆኑ ሌሎቹን ሁሉ ደመሰሳቸው:: የእርሷም በቤታችን ውስጥ ሠራተኛ መሆን ቅንጣት ታህል ቅር አላሠኘኝም፡፡
አንዳንድ ጊዜ ያቺ በውስጤ የምትፍለከለከዋ ጤዛ የምታህል ወኔዬ
ድንገት በምትገነፍልበት ጊዜ «ከዛሬ ጀምሮ ከትክክለኛ አመለካከት ውጭ
የሆነውን አስተሳሰብ ለመቋቋምና ለመበረቃቀስ ቆራጩ እነሣለሁ፡፡ በወዲያነሽ የተነሣ ምንም ዐይነት መጥፎ ሁኔታና አደጋ ቢደርስብኝ ግንባሬን አላጥፍም፡፡
«ከእንግዲህ ወዲያ የትልቅ ሰው ልጅ አጥንተ ጥሩ እና ደመ ንጹሕ
በሚለው ከንቱ አሮጌ እምነት በጭራሽ አላምንም፡፡ በእኔና በእርሷ መካከል የኑሮ
ደረጃ፣ ሀብታምና ድሃ ሆኖ የመወለድ ልዩነት እንጂ በተፈጥሮ ሰዉነት መበላለጥ ስለ ሌለ እስከ ዘለቄታው ከእርሷ ጋር መኖር እችላለሁ፡፡
«የአስተሳሰባችን ያለ መቀራረብ የሚያስከትለውም ችግር እንዲወገድ
የጋራ ጥረት ማድረግ ይቻላል፡፡ እኔና እርሷ በሰውነታችን ፍፁም እኩል መሆናችንን እኔዉ ለእኔ ማረጋገጥና ማሳወቅ ይኖርብኛል» እያልኩ በሐሳብ ሽቅብ
እመጥቅና እንደገና ደግሞ ቁልቁል ወርጄ ዘጭ እላለሁ፡፡ በሐሳብ ሠረገላ ላይ
ተቀምጩ የሐሳብ ልጓም ስስብና ስለቅ አያሌ ቀናት ዐለፉ፡፡
እናቴ ከራት በኋላ የተፈላውን ቡና እንዳከተመች ከተቀመጠችበት
ትንቡኬ ወንበር ላይ በዝግታ ተነሥታ ከደረቷ
👍5
ውስጥ የተቋጠረ መሐረብ
አወጣች፡፡ ቁም ነገረኛነትን ለመግለጽ በሚውተረተሩ ቃላት ለመናገር ፊቷን
ፈገግታ እየነሣች የድሃ ጉልበት ጥሩ አይደለም ልጄ! የድሃ እንባም ለልጅና
ለልጅ ልጅ ይቆያል፡፡ ትውሰድና ያፈቀዳትን ታድርገው፡ ይኸውልህ የአራት ወር
ደሞዟ» ብላ በመሐረብ የተቋጠረ ገንዘብ ጥላልኝ ወደ መኝታ ቤት ገባች። ከራት
በኋላ የውብነሽ ወደ መኝታ ቤቷ ስትገባ እኔም ወደ ክፍሏ ሄድኩ፡፡ የደሞዝ
መፈረሚያውን መዝገብ አውጥቼ አጭሯን የደመወዜን ተቀብያለሁ ሐተታ
ከጻፍኩ በኋላ የወዲያነሽን እንደ ተለመደው ጠራኋት፡፡
በጻፍኩት ውስጥ ተጨማሪው አዲስ ነገር፡ ላለፉት አራት ወሮች ጉልበቷ
ለእያንዳንዱ ወር የአንድ ብር ጭማሪ ማግኘቷ ብቻ ነበር፡፡
እንደ ቀድሞው ሳይሆን በጣም ተጠግታ አጠገቤ ቆመች፡፡ ደሞዟ ከፌት ለፊቷ ተቀምጦ ነበር፡፡ የቀኝ እጅ አውራ ጣቷን ነጥዩ ይዤ ቀለም ልለቀልቃት እጄን ሾል ሾል ሳደርግ አውራ ጣቷን ከእጄ ውስጥ እሾለከቻት፡፡ ጣቷን ወደ ውስጥ ዐጥፋ ባራቱ ጣቶቿ ሥር ቆለፈቻት፡፡ በአካባቢው ሰው ያለመኖሩን ቀደም ብላ በማረጋገጧ በሩን ዘጋችው:: ከዚያም ጎንበስ ብላ የተጻፈውን ጽሑፍ አንጠርጥራ አነበበችው:: የያዝኩትን ብዕር ወስዳ ከጽሑፉ በስተቀኝ ግርጌ
«የወዲያነሽ አሽናፊ» ብላ እሳምራ ጻፈች፡፡ ብዕሩን ጣል አድርጋ ትከሻዬን ተመርኩዛ ቆመች፡፡ ለምን እንደሆነ ባላውቅም ደነገጥኩ። ያየሁትን ማመን አቃተኝ፡፡ ለመቀመጥም ለመነሣትም ዐቅም አጣሁ፡፡ መንፈሴን አንዳች አስደሳች
ነገር ከወዲያ ወዲህ ናጣት፡፡ ቀና አልኩና ትኩር ብዬ ተመለከትኳት፡፡ በፊቷ ላይ
የተለመደው እንጂ ልዩና አዲስ ፈገግታ አልታየባትም።
እኔ ግን ስለ አዲሷ «እሷ» ሳስብና በማላውቀው የሕይወቷ ምስጢር
ውስጥ ስጠልምና ስወጣ ጥቂት ደቂቃዎች አለፉ፡፡ ማንበብና መጻፍ የምትችል በመሆኗ ወሰን የለሽ ደስታና ተስፋ አጥለቀለቀኝ። ወዲያው 'ለምን? ብባል ወዲያው መልስ መስጠት አልችልም።
የአቀማመጤን አቅጣጫ ቀይሬ የወዲያነሽ ከፊት ለፊቴ እንድትቆም
አደረግሁ፡፡ ከዚያም ሁለቱንም እጆቿን ይዤ አንጋጥጬ እያየሁ «የወዲያነሽ የት
ተማርሽ? ማን አስተማረሽ?» ብዬ ባጭሩ ጠየቅኋት፡፡ ፈገግታዋ ውስጥ ውስጡን
ለሚንፈቀፈቀው የደስታ ስሜት እጁን ሰጠ፡፡ ውብ ማራኪ ድምጿም ሰለለ።
«ወይኔ ተላሊት! አንተን ያስደሰትኩ መስሎኝ ተሳሳትኩ» ብላ ከንፈሯን
መጠጠች። ከጥቂት ዝምታ በኋላ «ከተውኩት ይኸው እንግዲህ ከሁለት ዓመት በላይ ሊሆን ነው» ብላ አሁንም እንደገና ትንፋሿን አንዳች ዝም አርጌ ነገር ወደ ውስጥ የመጠጠው ይመስል በዚያው ጸጥ አለች።
«እናሳ?» ብዩ ከያዛት የዝምታ ወጥመድ ባላላቅቃት ኖሮ ዝምታዋ በዚያው ማርኮ ሊያስቀራት ነበር፡፡ «ምኑን እናሳ' አልከኝ፡ አሁን እንዲህ ውሃ በልቶት ሊቀር ለወጉ ያህል እስከ ሰባተኛ ክፍል ተምሬ ነበር» ብላ ትጨርስ እንባ ካረገዙት ዐይኖቿ ላይ የእንባ እንክብሎች እየተሽቀዳደሙ ወረዱ፡፡
ኀዘኗና እንባዋ የልቤን ጣራና ወጋግራ አነቃነቀው:: አንጀቴ ተላወሰ፡ ነፍሴ ሰተት ብላ ትካዜ ረግረግ ውስጥ ተዘፈቀች፡፡
ገንዘቡን አንስታ ከቆጠረች በኋላ ኀዘን ባደቅቃት ድምዕ “እንካ አንተው ጋ
አስቀምጥልኝ» ብላ ኮቴ ኪሴ ውስጥ ወሽቃው ጥላኝ ወጣች።
አንዳንድ ቀን ማንም ሳይሰማና ሳያውቅ ወደ መኝታ ቤት እየገባች ከእኔ ጋር ማደሯ በታላቅ ጥንቃቄ ቀጠለ። ሆኖም ሁል ጊዜ በሕሊና ዐይኖቼ ፊት ፈታኝ የሆነ የውድቀት ፈተና እንጂ የተስፋ ውጋገን አልታየኝ አለ፡፡
የፈጸምኩትንና ያጋጠመኝን ነገር ሁሉ ብቻዬን ስለተሸከምኩት የሐሳብ ጭነት ከበደኝ፡፡ ምስጢሬን አፍኜ እስከወዲያኛው ለመዝለቅ ያለኝ ቆራጥነትና ብርታት እንደ ትቢያ በነነ፡፡ አካላቴ በሥጋት ተመነጠረ፡፡
አስፈላጊውን ምክርና ብልሃት ወይም ሌላ ርዳታ ሊያገኝልኝና ሊያደርግልኝ፡ የወዲያነሽንም ከመከራ ለማዳን የሚቻልበትን ቀና ሐሳብ ሊያካፍለኝ የሚችለው ልብ ሰፊዉ የልብ ጓደኛዬ ጉልላት ብቻ እንደሆነ ተገነዘብኩ፡፡....
💫ይቀጥላል💫
ግን እንዴት ነው ድርሰቱ እየተመቻቹ ነው? ዝም አላችሁ እኮ እስኪ አብሮነታችሁን Like 👍 በማድረግ አሳውቁኝ።
አወጣች፡፡ ቁም ነገረኛነትን ለመግለጽ በሚውተረተሩ ቃላት ለመናገር ፊቷን
ፈገግታ እየነሣች የድሃ ጉልበት ጥሩ አይደለም ልጄ! የድሃ እንባም ለልጅና
ለልጅ ልጅ ይቆያል፡፡ ትውሰድና ያፈቀዳትን ታድርገው፡ ይኸውልህ የአራት ወር
ደሞዟ» ብላ በመሐረብ የተቋጠረ ገንዘብ ጥላልኝ ወደ መኝታ ቤት ገባች። ከራት
በኋላ የውብነሽ ወደ መኝታ ቤቷ ስትገባ እኔም ወደ ክፍሏ ሄድኩ፡፡ የደሞዝ
መፈረሚያውን መዝገብ አውጥቼ አጭሯን የደመወዜን ተቀብያለሁ ሐተታ
ከጻፍኩ በኋላ የወዲያነሽን እንደ ተለመደው ጠራኋት፡፡
በጻፍኩት ውስጥ ተጨማሪው አዲስ ነገር፡ ላለፉት አራት ወሮች ጉልበቷ
ለእያንዳንዱ ወር የአንድ ብር ጭማሪ ማግኘቷ ብቻ ነበር፡፡
እንደ ቀድሞው ሳይሆን በጣም ተጠግታ አጠገቤ ቆመች፡፡ ደሞዟ ከፌት ለፊቷ ተቀምጦ ነበር፡፡ የቀኝ እጅ አውራ ጣቷን ነጥዩ ይዤ ቀለም ልለቀልቃት እጄን ሾል ሾል ሳደርግ አውራ ጣቷን ከእጄ ውስጥ እሾለከቻት፡፡ ጣቷን ወደ ውስጥ ዐጥፋ ባራቱ ጣቶቿ ሥር ቆለፈቻት፡፡ በአካባቢው ሰው ያለመኖሩን ቀደም ብላ በማረጋገጧ በሩን ዘጋችው:: ከዚያም ጎንበስ ብላ የተጻፈውን ጽሑፍ አንጠርጥራ አነበበችው:: የያዝኩትን ብዕር ወስዳ ከጽሑፉ በስተቀኝ ግርጌ
«የወዲያነሽ አሽናፊ» ብላ እሳምራ ጻፈች፡፡ ብዕሩን ጣል አድርጋ ትከሻዬን ተመርኩዛ ቆመች፡፡ ለምን እንደሆነ ባላውቅም ደነገጥኩ። ያየሁትን ማመን አቃተኝ፡፡ ለመቀመጥም ለመነሣትም ዐቅም አጣሁ፡፡ መንፈሴን አንዳች አስደሳች
ነገር ከወዲያ ወዲህ ናጣት፡፡ ቀና አልኩና ትኩር ብዬ ተመለከትኳት፡፡ በፊቷ ላይ
የተለመደው እንጂ ልዩና አዲስ ፈገግታ አልታየባትም።
እኔ ግን ስለ አዲሷ «እሷ» ሳስብና በማላውቀው የሕይወቷ ምስጢር
ውስጥ ስጠልምና ስወጣ ጥቂት ደቂቃዎች አለፉ፡፡ ማንበብና መጻፍ የምትችል በመሆኗ ወሰን የለሽ ደስታና ተስፋ አጥለቀለቀኝ። ወዲያው 'ለምን? ብባል ወዲያው መልስ መስጠት አልችልም።
የአቀማመጤን አቅጣጫ ቀይሬ የወዲያነሽ ከፊት ለፊቴ እንድትቆም
አደረግሁ፡፡ ከዚያም ሁለቱንም እጆቿን ይዤ አንጋጥጬ እያየሁ «የወዲያነሽ የት
ተማርሽ? ማን አስተማረሽ?» ብዬ ባጭሩ ጠየቅኋት፡፡ ፈገግታዋ ውስጥ ውስጡን
ለሚንፈቀፈቀው የደስታ ስሜት እጁን ሰጠ፡፡ ውብ ማራኪ ድምጿም ሰለለ።
«ወይኔ ተላሊት! አንተን ያስደሰትኩ መስሎኝ ተሳሳትኩ» ብላ ከንፈሯን
መጠጠች። ከጥቂት ዝምታ በኋላ «ከተውኩት ይኸው እንግዲህ ከሁለት ዓመት በላይ ሊሆን ነው» ብላ አሁንም እንደገና ትንፋሿን አንዳች ዝም አርጌ ነገር ወደ ውስጥ የመጠጠው ይመስል በዚያው ጸጥ አለች።
«እናሳ?» ብዩ ከያዛት የዝምታ ወጥመድ ባላላቅቃት ኖሮ ዝምታዋ በዚያው ማርኮ ሊያስቀራት ነበር፡፡ «ምኑን እናሳ' አልከኝ፡ አሁን እንዲህ ውሃ በልቶት ሊቀር ለወጉ ያህል እስከ ሰባተኛ ክፍል ተምሬ ነበር» ብላ ትጨርስ እንባ ካረገዙት ዐይኖቿ ላይ የእንባ እንክብሎች እየተሽቀዳደሙ ወረዱ፡፡
ኀዘኗና እንባዋ የልቤን ጣራና ወጋግራ አነቃነቀው:: አንጀቴ ተላወሰ፡ ነፍሴ ሰተት ብላ ትካዜ ረግረግ ውስጥ ተዘፈቀች፡፡
ገንዘቡን አንስታ ከቆጠረች በኋላ ኀዘን ባደቅቃት ድምዕ “እንካ አንተው ጋ
አስቀምጥልኝ» ብላ ኮቴ ኪሴ ውስጥ ወሽቃው ጥላኝ ወጣች።
አንዳንድ ቀን ማንም ሳይሰማና ሳያውቅ ወደ መኝታ ቤት እየገባች ከእኔ ጋር ማደሯ በታላቅ ጥንቃቄ ቀጠለ። ሆኖም ሁል ጊዜ በሕሊና ዐይኖቼ ፊት ፈታኝ የሆነ የውድቀት ፈተና እንጂ የተስፋ ውጋገን አልታየኝ አለ፡፡
የፈጸምኩትንና ያጋጠመኝን ነገር ሁሉ ብቻዬን ስለተሸከምኩት የሐሳብ ጭነት ከበደኝ፡፡ ምስጢሬን አፍኜ እስከወዲያኛው ለመዝለቅ ያለኝ ቆራጥነትና ብርታት እንደ ትቢያ በነነ፡፡ አካላቴ በሥጋት ተመነጠረ፡፡
አስፈላጊውን ምክርና ብልሃት ወይም ሌላ ርዳታ ሊያገኝልኝና ሊያደርግልኝ፡ የወዲያነሽንም ከመከራ ለማዳን የሚቻልበትን ቀና ሐሳብ ሊያካፍለኝ የሚችለው ልብ ሰፊዉ የልብ ጓደኛዬ ጉልላት ብቻ እንደሆነ ተገነዘብኩ፡፡....
💫ይቀጥላል💫
ግን እንዴት ነው ድርሰቱ እየተመቻቹ ነው? ዝም አላችሁ እኮ እስኪ አብሮነታችሁን Like 👍 በማድረግ አሳውቁኝ።
👍6
#ሕልመኛ_ተጓዥ
( .. ተቀበል . . . )
በመንገድኽ ኹሉ ዕንቅፋት አትፍራ
ተማርበት እንጂ በእውቀት አትኩራ።
መውደቅኽ ምሳሌ ፣ ሸክፈው እንደ ጓዝ።
ድሎትን አትውደድ ፣ የንዋይን ጉዝጓዝ፡፡
ስሕተትኽን ግደፍ ፤ መርምር በረቂቁ
በመጠረቡ ነው ፤ አልማዝ ማብረቅረቁ፡፡
የጅራፍ ቁግ አጥብቅ ፤ ግመድ አታቅማማ
ካልገረፉት አይጮኽ ፣ ካልጮኸ አይሰማ።
ደዌን አትሽሸው ፣ መርምር በጽሞና
ከችግር አይደል ወይ? መፍትሔ ሚጠና።
አስተውል ፣ ተመልከት! መርምር በአርምሞ
ማንም ሰው አይድንም! ካልታመመ ቀድሞ።
(ደዌን አትሽሸው ፣ ይልቅስ መርምረው
ከመታመም ላይ ነው! መድኅን ሚገኘው።)
“የሕልሜ ሳቢሳ፤
ሾተልኽን አንሣ
ሊበላኝ ነበረ ፣ ቶሎ ባልነሣ።
የሕልሜ ነብር
ይብላኝ ነበረ ፣ ተኝቼ ብቀር።”
ይህ ነው ያ'ንተ ግጥም!
ይህ ነው ያ'ንተ ዜማ !
በነቂስ አትመን . . .!
ግምትም አትጣ . . .!
ልብኽንም ስማ።
ይህ ነው ያ'ንተ ዜማ !
ይህ ነው ያ'ንተ ግጥም !
ያለ መሰናክል፣
ያለ አንዳች ዕክል፣
ሕይወት ፍጹም አይጥም።
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
( .. ተቀበል . . . )
በመንገድኽ ኹሉ ዕንቅፋት አትፍራ
ተማርበት እንጂ በእውቀት አትኩራ።
መውደቅኽ ምሳሌ ፣ ሸክፈው እንደ ጓዝ።
ድሎትን አትውደድ ፣ የንዋይን ጉዝጓዝ፡፡
ስሕተትኽን ግደፍ ፤ መርምር በረቂቁ
በመጠረቡ ነው ፤ አልማዝ ማብረቅረቁ፡፡
የጅራፍ ቁግ አጥብቅ ፤ ግመድ አታቅማማ
ካልገረፉት አይጮኽ ፣ ካልጮኸ አይሰማ።
ደዌን አትሽሸው ፣ መርምር በጽሞና
ከችግር አይደል ወይ? መፍትሔ ሚጠና።
አስተውል ፣ ተመልከት! መርምር በአርምሞ
ማንም ሰው አይድንም! ካልታመመ ቀድሞ።
(ደዌን አትሽሸው ፣ ይልቅስ መርምረው
ከመታመም ላይ ነው! መድኅን ሚገኘው።)
“የሕልሜ ሳቢሳ፤
ሾተልኽን አንሣ
ሊበላኝ ነበረ ፣ ቶሎ ባልነሣ።
የሕልሜ ነብር
ይብላኝ ነበረ ፣ ተኝቼ ብቀር።”
ይህ ነው ያ'ንተ ግጥም!
ይህ ነው ያ'ንተ ዜማ !
በነቂስ አትመን . . .!
ግምትም አትጣ . . .!
ልብኽንም ስማ።
ይህ ነው ያ'ንተ ዜማ !
ይህ ነው ያ'ንተ ግጥም !
ያለ መሰናክል፣
ያለ አንዳች ዕክል፣
ሕይወት ፍጹም አይጥም።
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
👍2
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....“ትሬይን ያስገደልከው አንተ ነህ አይደል?”
ብላ ኒኪ መሳሪያውን በድጋሚ አንስቶ ሊተኩስባት በተዘጋጀው ሉዊስ
ላይ አፍጥጣ እየተመለከተች ጠየቀችው።
ስለ አኔ ካወራት በኋላ ቅናቱ በጣም ስለጨመረበት እና ስለተናደደ እሷን
ቶሎ ገድሎ ለመገላገል ፈልጓል። የኒኪ ብቸኛ ተስፋ ደግሞ እሱ ወሬውን
እንዳያቋርጥ በማድረግ ለትንሽ ደቂቃም ቢሆን በህይወት መቆየት እንድትችል ማድረግ ነው። መቆየት ደጉ ይባል አይደል?
መሳሪያውን ወደ ታች አውርዶ ሉዊስ አይኑን እያንከባለለ ከተመለከታት በኋላ
እሱ በጣም ደደብ ልጅ ነው። ቢፈልግ ኖሮ በህይወት መቆየት ይችል ነበር። እያንዳንዱን ዕድል ሰጥተነው ነበር፡፡”
“ምን ማለትህ ነው “እያንዳንዱን ዕድል ስትል? የምን እድል? ገንዘብ ተበድሮህ ነበር እንዴ?” አለችው የዴሪክ ዊሊያምስ ትሬይ ዌስትመንት ውስጥ በዕፅ አዘዋዋሪነት ይሰራ ነበር ያላትን ነገርን እና እንዲሁም ደግሞ የዊሊ ባደን አፍ ውስጥ የተጎስጎሱትን ገንዘቦች አስታውሳ
“ትንሽ ብር ነበረበት ግን ለዚያ ብዬ አልነበረም ያስወገድኩት” አላት፡፡
“እና ለምንድን ነው ታዲያ? አዲስ ህይወት በመጀመሩ ተናደህ ነው?
ከሱስ በመፅዳቱ እና ከወሮበላ ቡድኖች ጋር መሥራት ስላቆመ ነው?”
ሉዊስም ፈገግ ካለ በኋላ “ዶክተር ሮበርትስ እኔ ስለ ትሬይ ሬይሞንድ
ህይወት ያን ያህል የሚያገባኝ ከመሰለሽ ተሳስተሻል፡፡ እኔ የቢዝነስ ሰው ነኝ፡፡
ትሬይ ደግሞ የእኔ ድርጅት ቤተሰብ አይደለም፡፡ እሱ የዕፅ ተጠቃሚ ነው።
ማለቴ ገዢ ነው፡፡ ገዢ ሲሄድ ደግሞ ሌላ ገዢ ይመጣል።” ኒኪም ኮስተር
ብላ እያየችው “ትሬይ በጣም ተሰቃይቶ ነው እንዲሞት የተደረገው። ምን
ቢበድልህ ነው ይህንን ያስደረግከው?”
ሮድሪጌዝ በስልቹነት ስሜት ሲያዛጋ ስታየው ከውስጧ ሀይለኛ ንዴት
እና ጥላቻ እየተግተለተለ ሲወጣ ይሰማታል፡፡ በውስጧም አኔ እንዴት ነው
ይህንን አውሬ ሰው አፍቅራው ልታገባው የቻለችው?' ብላ አሰበች።
“ሬይ ሬይሞንድ ጋ እኔ የምፈልገው አንድ ነገር ነበር።” አላት እና ሉዊስ በመቀጠልም “ለዚያም ልዋጭ ጥሩ ዋጋን አቅርቤለት ነበር፡፡ እሱ ግን
እምቢ ብሎ ደረቀ፡፡ ይሄ ደግሞ ለሞት የሚያበቃው ስህተቱ ነው።”
“ሬይ ጋ ያለ አንተ የምትፈልገው ነገር ምንድን ነበር?” ብላ ኒኪ ጠየቀችው በኋላ ወዲያውኑ አይኗ በእምባ ተሞላ። በጣም ብዙ አሰቃቂ ነገሮች በዙሪያዋ ተከስቶባት ስለነበር የትሬይን ሞት እና በእሱ ሞት ምክንያት የተሰማትን ግብር እና ሀዘን ከእሷ ገፍታ አስወግዳው ነበር። አሁን ግን ሞት ደጃፍ ላይ ስለቆመች ነው መሰል ሀዘኑ እና ሽብሩ ሁለመናዋን
ተቆጣጠሩት፡፡ “አንተ በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር አለህ፡፡ ትሬይ ግን
ምንም የለውም! በጣም ውድ የሚባለው ዕቃው እኮ ዶውግ የገዛለት የመንገድ ላይ መንሸራተቻው (ስኬት ቦርዱ) ብቻ ነበር” አለችው በምሬት፡፡
“መረጃ ነበረው:: ማለትም አንቺ በቢሮሽ ውስጥ ሚስቴን ቴራፒ ስታደርጊ እሷን አስመልክቶ የምትወስጂውን የማስታወሻ ፅሁፍ እንዲሰጠኝ በትህትና ጠይቄው ነበር፡፡ እምቢ አለ ገደልኩት” አላት፡፡
“ግን እኮ እሱ ምንም አያውቅም” ብላ አየር ሳበች እና
“የእኔ እና የእሷን ምልልስን አስመልክቶ እኮ ማስታወሻ አልይዝም ነበር”
አለችው።
“ውሸታም!” ብሎ ጮኸባት እና “አንቺ ማስታወሻ ትይዢ ነበር::
የማስታወሻዎችሽ ኮፒዎች ደግሞ ፖሊሶቹ ጋር እንዳሉ አውቃለሁ።” አላት::
“በእውነት ከእሷ ጋር የቴራፒ ህክምናዬን ሳደርግ ማስታወሻ አልይዝም
ነበር” ሉዊስም ግር ብሎት “ለምን?” አላት፡፡
“ምክንያቱም እሷ አትፈልግም ነበር፡፡ ግን መያዝ ነበረብኝ” አለችው እና ኒኪ ፀፀት ተሰማት፡፡ በመቀጠልም “ትሬይን እኮ ስትጠይቀው የነበረው እኮ ሊያገኘው የማይችለውን መረጃ ነበር፡፡ ማንም
ሰው ሊያገኘው አይችልምም፡፡ ምክንያቱም መረጃው እዚህ ውስጥ ነው የሚገኘው” ብላ በጣቷ ጭንቅላቷን እየተመተመች ነገረችው። ሉዊስ ለአፍታ ያህል ዝም ብሎ የሰማውን ነገር ሲያዳምጥ ከቆየና በጣም ከት ብሎ ከሳቀ በኋላ
“ይገርማል አስቂኞቹ የስህተት ሰማዕቶች እስከ አሁን ድረስ አላለቁም!” ብሎ በሳቁ ብዛት የፈሰሰውን እምባውን በአይኑ ላይ በአይበሉባው ከጠረገ በኋላ “ዶክተር ሮበርትስ ይህንን ነገር ስላሳወቅሽኝ በጣም ነው የማመሰግነው፡፡ የሚደነቅ ነገር ነው ባክሽ፡፡ ለማንኛውም የምትገደይበትን እውነተኛ ምክንያት አውቀሽ መሞትሽ መልካም ነው::” አላት እና ለሦስተኛ ጊዜ መሳሪያውን ፊቷ ላይ ሲደቅን ኒኪ ጊዜዋ እንዳበቃ ገባት፡፡
“እንግዲህ ሁሉም ቲያትሮች በመጨረሻ ላይ የሆነ ጥሩ መዝጊያዐይኖራቸዋል፡፡ ደህና ሁኚ ዶክተር ሮበርት”
“ነፍስህ በገሃነም ይቃጠል!” ብላ ጮኸችበት ኒኪ፡፡
ከዚያም አንድ ጆሮ የሚያደነቁር ፍንዳታ ተሰማ እና ሁሉም ነገር ጨለማ ሆነ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በመጀመሪያ ጭለማው ተቆጣጠራት፡፡
ከዚያም ሁሉ ነገር ፀጥ አለ፡፡
ምንም አይነት ትንፋሽ፤ ምንም አይነት እንቅስቃሴ የለም፡፡ በቃ ሁሉም
ነገር ፀጥ ብሏል፡፡
ሰላም ብቻ::
እና ሞት እንደዚህ ነው ማለት ነው?'
ጨለማው እንዳለ ቢሆንም የልብ ምቷ ለራሷ ይሰማታል፡፡ ልክ ከረዥም
እንቅልፍ እንደሚነቃ እንስሳ ሁሉ እየተንጠራራች ነቃች፡፡ ስትነቃ ግን
ህመሙ ተሰማት፤ ያውም በደንብ ስል እና በጣም እሳት ሆኖ።
እግሬን' ብላ እጇን ወደ ታች ስትሰድ ሙቁ የሚያጣብቅ ደሟ ተቀበላት። ስለሆነም ጨለማው ራሷን በመሳቷ ሳይሆን የአዳራሹ መብራት በመጥፋቱ ምክንያት የመጣ እንደሆነ ገባት፡፡ ምንም እንኳን ኒኪ በእግዚአብሔር ባታምንም የሆነ ተዓምር መብራቱን እንዳጠፋላትና ሉዊስም በዚህ ግራ ተጋብቶ ተሳስቶ እግሯን እንደመታት ግልፅ ሆነላት። ምን ያህል ደም እንደፈሰሳት እያሰበችም እጇን ወደ ቁስሉ ስትልክ አመማት እና ቀጭን
ነው ድምፅ አወጣች፡፡
ድምፅ ማውጣቷ ስህተት ነበር፡፡ ይሄኔም ሉዊስ ድምፁን ወደሰማበት አቅጣጫ የእውር ድንብሩን ሲንቀሳቀስ ሰማች፡፡ ወዲያውኑ ግን ወለሉ ላይ
ስለወደቀ በስፓኒሽ ሲራገም ሰማች። ተጎድቶ ይሆን? በፍፁም፡፡ ምክንያቱም
መናገር ሲጀምር ድምፁ ጥርት ያለ ነበር። ድምፁ ውስጥ ህመምም ሆነ
ንዴት አይሰማም፡፡
“አንቺ ሸርሙጣ! ሰምቼሻለሁ”
ዝም ብላ ቆየች፡፡ በጣም ቀርቧታል፡፡ ምናልባትም አጠገቧ ሊደርስ አንድ
እርምጃ ብቻ ይሆናል የሚቀረው፡፡
“እየመጣሁልሽ ነው!”
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የጨለመው በጥልቅ እና በፍጥነት ነበር፡፡
ምድር ቤት የሚገኘው ዋናውን ፊዩዝ ያጠፋው ሉዊስን እና ፎቁ ውስጥ
ሊገኙ የሚችሉ የሉዊስ ሰዎችን ለማደናበር አስቦ ነው:: ይህን በማድረጉም ትንሽ የመዘጋጂያ ጊዜ ይኖረዋል፡፡ ጨለማው ሲውጠው ግን ጉድማን መብራቱን በማጥፋቱ ተፀፀተ።
ምድር ቤት ውስጥ አንገቱን አቀርቅሮ በጉልበቱ ተንበርክኮ ነው፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ ጭለማው እና የምድር ቤቱ እምክ እምክ መሽተት ልክ የሬሳ ሳጥን ውስጥ ያለ መሰለው፡፡ ምንም አይነት ብርሃን የለም፧ ስለዚህ ማምለጥ አይችልም፡፡ ልቡ በጣም መምታት ጀመረ። ስለዚህም ቶሎ ቶሎ አየር በማስወጣት እና በማስገባት ራሱን እንደምንም ብሎ ለማረጋጋት ቻለ::
“አሁን አስብ' ብሎ ለራሱ ተናገረ፡፡
የሱሪ ኪሱ ውስጥ ስልኩን መፈለግ ጀመረ ሁሉንም ኪሶች ሲፈትሻቸው ስልኩን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ቢሮ ትቶት እንደመጣ ገመተ በመቀጠልም የመኪናው ቁልፍ ላይ ማግላይት
እንዳለው አስታወሰ እና ከኪሱ አውጥቶ አበራው፡፡ ምድር ቤቱ ጣራ ላይ
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....“ትሬይን ያስገደልከው አንተ ነህ አይደል?”
ብላ ኒኪ መሳሪያውን በድጋሚ አንስቶ ሊተኩስባት በተዘጋጀው ሉዊስ
ላይ አፍጥጣ እየተመለከተች ጠየቀችው።
ስለ አኔ ካወራት በኋላ ቅናቱ በጣም ስለጨመረበት እና ስለተናደደ እሷን
ቶሎ ገድሎ ለመገላገል ፈልጓል። የኒኪ ብቸኛ ተስፋ ደግሞ እሱ ወሬውን
እንዳያቋርጥ በማድረግ ለትንሽ ደቂቃም ቢሆን በህይወት መቆየት እንድትችል ማድረግ ነው። መቆየት ደጉ ይባል አይደል?
መሳሪያውን ወደ ታች አውርዶ ሉዊስ አይኑን እያንከባለለ ከተመለከታት በኋላ
እሱ በጣም ደደብ ልጅ ነው። ቢፈልግ ኖሮ በህይወት መቆየት ይችል ነበር። እያንዳንዱን ዕድል ሰጥተነው ነበር፡፡”
“ምን ማለትህ ነው “እያንዳንዱን ዕድል ስትል? የምን እድል? ገንዘብ ተበድሮህ ነበር እንዴ?” አለችው የዴሪክ ዊሊያምስ ትሬይ ዌስትመንት ውስጥ በዕፅ አዘዋዋሪነት ይሰራ ነበር ያላትን ነገርን እና እንዲሁም ደግሞ የዊሊ ባደን አፍ ውስጥ የተጎስጎሱትን ገንዘቦች አስታውሳ
“ትንሽ ብር ነበረበት ግን ለዚያ ብዬ አልነበረም ያስወገድኩት” አላት፡፡
“እና ለምንድን ነው ታዲያ? አዲስ ህይወት በመጀመሩ ተናደህ ነው?
ከሱስ በመፅዳቱ እና ከወሮበላ ቡድኖች ጋር መሥራት ስላቆመ ነው?”
ሉዊስም ፈገግ ካለ በኋላ “ዶክተር ሮበርትስ እኔ ስለ ትሬይ ሬይሞንድ
ህይወት ያን ያህል የሚያገባኝ ከመሰለሽ ተሳስተሻል፡፡ እኔ የቢዝነስ ሰው ነኝ፡፡
ትሬይ ደግሞ የእኔ ድርጅት ቤተሰብ አይደለም፡፡ እሱ የዕፅ ተጠቃሚ ነው።
ማለቴ ገዢ ነው፡፡ ገዢ ሲሄድ ደግሞ ሌላ ገዢ ይመጣል።” ኒኪም ኮስተር
ብላ እያየችው “ትሬይ በጣም ተሰቃይቶ ነው እንዲሞት የተደረገው። ምን
ቢበድልህ ነው ይህንን ያስደረግከው?”
ሮድሪጌዝ በስልቹነት ስሜት ሲያዛጋ ስታየው ከውስጧ ሀይለኛ ንዴት
እና ጥላቻ እየተግተለተለ ሲወጣ ይሰማታል፡፡ በውስጧም አኔ እንዴት ነው
ይህንን አውሬ ሰው አፍቅራው ልታገባው የቻለችው?' ብላ አሰበች።
“ሬይ ሬይሞንድ ጋ እኔ የምፈልገው አንድ ነገር ነበር።” አላት እና ሉዊስ በመቀጠልም “ለዚያም ልዋጭ ጥሩ ዋጋን አቅርቤለት ነበር፡፡ እሱ ግን
እምቢ ብሎ ደረቀ፡፡ ይሄ ደግሞ ለሞት የሚያበቃው ስህተቱ ነው።”
“ሬይ ጋ ያለ አንተ የምትፈልገው ነገር ምንድን ነበር?” ብላ ኒኪ ጠየቀችው በኋላ ወዲያውኑ አይኗ በእምባ ተሞላ። በጣም ብዙ አሰቃቂ ነገሮች በዙሪያዋ ተከስቶባት ስለነበር የትሬይን ሞት እና በእሱ ሞት ምክንያት የተሰማትን ግብር እና ሀዘን ከእሷ ገፍታ አስወግዳው ነበር። አሁን ግን ሞት ደጃፍ ላይ ስለቆመች ነው መሰል ሀዘኑ እና ሽብሩ ሁለመናዋን
ተቆጣጠሩት፡፡ “አንተ በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር አለህ፡፡ ትሬይ ግን
ምንም የለውም! በጣም ውድ የሚባለው ዕቃው እኮ ዶውግ የገዛለት የመንገድ ላይ መንሸራተቻው (ስኬት ቦርዱ) ብቻ ነበር” አለችው በምሬት፡፡
“መረጃ ነበረው:: ማለትም አንቺ በቢሮሽ ውስጥ ሚስቴን ቴራፒ ስታደርጊ እሷን አስመልክቶ የምትወስጂውን የማስታወሻ ፅሁፍ እንዲሰጠኝ በትህትና ጠይቄው ነበር፡፡ እምቢ አለ ገደልኩት” አላት፡፡
“ግን እኮ እሱ ምንም አያውቅም” ብላ አየር ሳበች እና
“የእኔ እና የእሷን ምልልስን አስመልክቶ እኮ ማስታወሻ አልይዝም ነበር”
አለችው።
“ውሸታም!” ብሎ ጮኸባት እና “አንቺ ማስታወሻ ትይዢ ነበር::
የማስታወሻዎችሽ ኮፒዎች ደግሞ ፖሊሶቹ ጋር እንዳሉ አውቃለሁ።” አላት::
“በእውነት ከእሷ ጋር የቴራፒ ህክምናዬን ሳደርግ ማስታወሻ አልይዝም
ነበር” ሉዊስም ግር ብሎት “ለምን?” አላት፡፡
“ምክንያቱም እሷ አትፈልግም ነበር፡፡ ግን መያዝ ነበረብኝ” አለችው እና ኒኪ ፀፀት ተሰማት፡፡ በመቀጠልም “ትሬይን እኮ ስትጠይቀው የነበረው እኮ ሊያገኘው የማይችለውን መረጃ ነበር፡፡ ማንም
ሰው ሊያገኘው አይችልምም፡፡ ምክንያቱም መረጃው እዚህ ውስጥ ነው የሚገኘው” ብላ በጣቷ ጭንቅላቷን እየተመተመች ነገረችው። ሉዊስ ለአፍታ ያህል ዝም ብሎ የሰማውን ነገር ሲያዳምጥ ከቆየና በጣም ከት ብሎ ከሳቀ በኋላ
“ይገርማል አስቂኞቹ የስህተት ሰማዕቶች እስከ አሁን ድረስ አላለቁም!” ብሎ በሳቁ ብዛት የፈሰሰውን እምባውን በአይኑ ላይ በአይበሉባው ከጠረገ በኋላ “ዶክተር ሮበርትስ ይህንን ነገር ስላሳወቅሽኝ በጣም ነው የማመሰግነው፡፡ የሚደነቅ ነገር ነው ባክሽ፡፡ ለማንኛውም የምትገደይበትን እውነተኛ ምክንያት አውቀሽ መሞትሽ መልካም ነው::” አላት እና ለሦስተኛ ጊዜ መሳሪያውን ፊቷ ላይ ሲደቅን ኒኪ ጊዜዋ እንዳበቃ ገባት፡፡
“እንግዲህ ሁሉም ቲያትሮች በመጨረሻ ላይ የሆነ ጥሩ መዝጊያዐይኖራቸዋል፡፡ ደህና ሁኚ ዶክተር ሮበርት”
“ነፍስህ በገሃነም ይቃጠል!” ብላ ጮኸችበት ኒኪ፡፡
ከዚያም አንድ ጆሮ የሚያደነቁር ፍንዳታ ተሰማ እና ሁሉም ነገር ጨለማ ሆነ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በመጀመሪያ ጭለማው ተቆጣጠራት፡፡
ከዚያም ሁሉ ነገር ፀጥ አለ፡፡
ምንም አይነት ትንፋሽ፤ ምንም አይነት እንቅስቃሴ የለም፡፡ በቃ ሁሉም
ነገር ፀጥ ብሏል፡፡
ሰላም ብቻ::
እና ሞት እንደዚህ ነው ማለት ነው?'
ጨለማው እንዳለ ቢሆንም የልብ ምቷ ለራሷ ይሰማታል፡፡ ልክ ከረዥም
እንቅልፍ እንደሚነቃ እንስሳ ሁሉ እየተንጠራራች ነቃች፡፡ ስትነቃ ግን
ህመሙ ተሰማት፤ ያውም በደንብ ስል እና በጣም እሳት ሆኖ።
እግሬን' ብላ እጇን ወደ ታች ስትሰድ ሙቁ የሚያጣብቅ ደሟ ተቀበላት። ስለሆነም ጨለማው ራሷን በመሳቷ ሳይሆን የአዳራሹ መብራት በመጥፋቱ ምክንያት የመጣ እንደሆነ ገባት፡፡ ምንም እንኳን ኒኪ በእግዚአብሔር ባታምንም የሆነ ተዓምር መብራቱን እንዳጠፋላትና ሉዊስም በዚህ ግራ ተጋብቶ ተሳስቶ እግሯን እንደመታት ግልፅ ሆነላት። ምን ያህል ደም እንደፈሰሳት እያሰበችም እጇን ወደ ቁስሉ ስትልክ አመማት እና ቀጭን
ነው ድምፅ አወጣች፡፡
ድምፅ ማውጣቷ ስህተት ነበር፡፡ ይሄኔም ሉዊስ ድምፁን ወደሰማበት አቅጣጫ የእውር ድንብሩን ሲንቀሳቀስ ሰማች፡፡ ወዲያውኑ ግን ወለሉ ላይ
ስለወደቀ በስፓኒሽ ሲራገም ሰማች። ተጎድቶ ይሆን? በፍፁም፡፡ ምክንያቱም
መናገር ሲጀምር ድምፁ ጥርት ያለ ነበር። ድምፁ ውስጥ ህመምም ሆነ
ንዴት አይሰማም፡፡
“አንቺ ሸርሙጣ! ሰምቼሻለሁ”
ዝም ብላ ቆየች፡፡ በጣም ቀርቧታል፡፡ ምናልባትም አጠገቧ ሊደርስ አንድ
እርምጃ ብቻ ይሆናል የሚቀረው፡፡
“እየመጣሁልሽ ነው!”
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የጨለመው በጥልቅ እና በፍጥነት ነበር፡፡
ምድር ቤት የሚገኘው ዋናውን ፊዩዝ ያጠፋው ሉዊስን እና ፎቁ ውስጥ
ሊገኙ የሚችሉ የሉዊስ ሰዎችን ለማደናበር አስቦ ነው:: ይህን በማድረጉም ትንሽ የመዘጋጂያ ጊዜ ይኖረዋል፡፡ ጨለማው ሲውጠው ግን ጉድማን መብራቱን በማጥፋቱ ተፀፀተ።
ምድር ቤት ውስጥ አንገቱን አቀርቅሮ በጉልበቱ ተንበርክኮ ነው፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ ጭለማው እና የምድር ቤቱ እምክ እምክ መሽተት ልክ የሬሳ ሳጥን ውስጥ ያለ መሰለው፡፡ ምንም አይነት ብርሃን የለም፧ ስለዚህ ማምለጥ አይችልም፡፡ ልቡ በጣም መምታት ጀመረ። ስለዚህም ቶሎ ቶሎ አየር በማስወጣት እና በማስገባት ራሱን እንደምንም ብሎ ለማረጋጋት ቻለ::
“አሁን አስብ' ብሎ ለራሱ ተናገረ፡፡
የሱሪ ኪሱ ውስጥ ስልኩን መፈለግ ጀመረ ሁሉንም ኪሶች ሲፈትሻቸው ስልኩን ሊያገኝ አልቻለም፡፡ ቢሮ ትቶት እንደመጣ ገመተ በመቀጠልም የመኪናው ቁልፍ ላይ ማግላይት
እንዳለው አስታወሰ እና ከኪሱ አውጥቶ አበራው፡፡ ምድር ቤቱ ጣራ ላይ
👍3
በጣም ትልልቅ የአልሙኒየም ቱቦዎች በብሎን ከጣራው ጋር ታስረዋል፡፡ ከኋላው ወደ
ምድር ቤቱ የመጣበት እና ወደ ላይ ወደ ጠባቡ መንገድ የሚያወጣው ቱቦ
አለ። ከፊዩዝ ሳጥኑ ሃያ ጫማ ርቀት ላይ ደግሞ ከምድር ወደ ላይ የሚያወጣ የብረት ደረጃ (መሰላል) አለ፡፡
ጉድማን እየዳኸ ወደ መሰላሉ አመራ፡፡ ሁሉ ነገር ፀጥ ብሏል፡፡ መብራቱን ካጠፋ ከሰኮንዶች በኋላ የተኩስ ድምፅ ሰምቷል፤ ከዚያ በኋላ ግን ምንም ነገር ሊሰማ አልቻለም። ሉዊስ ሮድሪጌዝ ህንፃው ውስጥ ይሆን? ወይንስ ኒኪን ከገደላት በኋላ ህንፃውን ትቶ ወጥቶ ይሆን? “እንደዚያ ከሆነ ደግሞ ህንፃው ውስጥ ብቻዬን ነዋ የምገኘው?' ብሎ እያሰበ እያለ ከላይ ቀጭን የህመም ድምፅ ሰማ። “ኒኪ?” አለ እና ሽጉጡን ጨብጦ ወደ ላይ በመሰላሉ ላይ መውጣት ጀመረ፡፡
ሉዊስ ሮድሪጌዝ ልክ እንደ አዳኝ ተኩላ ፀጥ ብሎ ሲያዳምጥ ቆየ፡፡ አጠገቡ እንዳለች ይሰማዋል። ጥይቱ ስላቆሰላት ቶሎ ቶሎ ስትተነፍስ ይታወቀዋል፡፡
ሽጉጡን ጥብቅ አድርጎ እንደ ያዘ ድምፅ ወደሰማበት አቅጣጫ ተወረወረ፡፡ አንድ ጊዜ ካገኛት በኋላ አንገቷን አንቆ ጭንቅላቷን ወለሉ ላይ ይደፋዋል። ከዚያም ይሄንን የሚስቱን አኔን ልብ ሲመርዙበት የነበሩ ቃላትን ሲያወጣ የነበረ ጭንቅላቷን በጥይት ይበታትነዋል። በቃ ከዚያ በኋላ እሱ
እና አኔ በሰላም አብረው መኖር ይጀምራሉ።
“የት ነው ያለሺው?” ብሎም ወደ ፊት ተጠጋ። አሁን የትም ልታመልጠው አትችልም፡፡ ነገር ግን ወደ ፊት ሲጠጋ አየር እንጂ ምንም ነገር ሊያገኝ አልቻለም፡፡ 'የት አባቷ ነው የሄደችው?' አለ ለራሱ፡፡
ይሄኔም ሀይለኛ የሆነ ምት ከእግሮቼ መሀል ተሰማው፡፡ አዎን ድብን
ያለ ምት ቆለጡ ላይ ሲያርፍበት ህመሙ ከቁጥጥሩ በላይ ስለሆነበት ቆለጡን ታቅፎ ወደ ወለሉ ሸብረክ አለ። ከኋላውም ልክ አይጥ ወደ ጉድጓድ
ስትሮጥ የምታሰማው አይነት ድምፅ ተሰማው፡፡
'ወይኔ ይህቺ ሸርሙጣ በእግሬ ሥር ሾልካ አመለጠችኝ! አሁን በእርግጠኛነት ወደ ብረቶቹ ደረጃ ነው የምትሄደው! አለ ለራሱ፡፡
እንደምንም ብሎ ቀና አለና ጭለማው ውስጥ እየተኮሰ “እገድልሻለሁ!
እገድልሻለሁ!” እያለ ማጓራት ጀመረ፡፡
ተሳካልኝ! አመለጥኩኝ አለች ኒኪ ለራሷ፡፡
ኒኪ የተኩሶቹን ድምፅ የሰማቸው ለእሳት አደጋ መውጫ የተዘጋጀው ጫፍ ላይ ስትደርስ ነበር፡፡ ላይ ከደረሰች በኋላ በሩን ከፍታ በደረጃው ወደ ታች ወደ ምድር የሚያወርዳትን የብረት መሰላል ተመለከተች፡፡ ከታች ከውጪ በኩል የሚመጣ የምሽቱ ደብዘዝ ያለ ብርሃን ይታያታል። ታች ከወረደች በኋላ ቢያንስ የሆነ የሚረዳኝ ሰው አላጣም ብላ ኒኪ በተስፋ ተሞልታ መሰላሉን መውረድ ጀመረች፡፡ ከሁለት ደረጃዎች በኋላ ግን
በጥይት የተመታችው ቁስል ስቃይ ከመጠን በላይ ስለሆነባት የያዘችው
መስላል ከእጇ አምልጦ ወደ ታች ወረደ፡፡ “እግሬን” ብላ እየጮኸች ወደቀች፡፡
የመጀመሪያው ፎቅ ላይ ያለ ኮንክሪት ላይም አረፈች። ራሷን ለጥቂት
ሰኮንዶች ያህል ሳተችና ወደ ራሷ ተመለሰች። ወዲያውኑም ከኮንክሪቱ ጥግ ላይ ከሚገኝ አንድ ጓዳ መሰል ነገር ውስጥ እየተሳበች ገባች እና ጥቅልል
አለች።
ለአፍታ ያህል ከባድ ሀዘን ውስጧን ተሰማው፡፡ እምባዋም አይኗን ሞላው። አሁን ካለችበት ቦታ ሃያ ጫማ ያህል ወደ ታች የእሳት አደጋው መውጪያ በር ይታያታል፡፡ ለጥቂት ለማምለጥ ችላ ነበር፡፡ አሁን አንዱንም ጡንቻዋን ማንቀሳቀስ አትችልም፡፡ ስለዚህ ሮድሪጌዝ መጥቶ ይገድላታል። ከእንግዲህ ይህ ያለችበት የህይወቷ የመጨረሻ ክፍል ይሆናል ማለት ነው።
እዚያው ጥቅልል እንዳለች አይኗን ጨፈነች፡፡ ወዲያውኑም ያልጠበቀችው አይነት ሙቀት መላ ሰውነቷን ይሞቃት ጀመር፡፡ የሆነ ደስ የሚል ስሜትም ተሰማት። ውስጧ የነበረው ሀዘንም ፍርሃቷን እና የቁስሏን ህመም አስከትሎ ከውስጧ ተንኖ ሲወጣ ይታወቃታል። በምትኩም ወፍራም የድካም ብርድ ልብሱን ጫነባት፡፡
ተኚ ኒኪ፡፡ መተኛት አለብሽ አለች ለራሷ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ጉድማን የመስላሉ ጫፍ ላይ ከደረሰ በኋላ ወደ ላይ ተስቦ ወለሉ ላይ ወጣ፡፡ ክፍሉ ውስጥ በሚገኙት ከሁለቱ የቆሽሹ መስኮቶች የሚገባው ብርሃን የምሽቱን ደብዛዛ ብርሃን ወደ ውስጥ ያስገባሉ፡፡ ምድር ቤቱ ከዚህ በጣም ጭለማ ስለነበረ ግን አይኑ ወዲያው ነበር የተላመደው:: እና ማግላይቱን አጠፋው። ክፍሉ ትልቅ እና ባዶ መሆኑን ሲመለከት በደንብ ተረጋጋ።
በመቀጠልም ወደ ላይኛው ፎቅ ወደሚያወጣ አሳንሰር እየተንቀሳቀሰ እያለ ከታች ከምድር ቤቱ የሚያውቀው ድምፅ ስሙን ሲጠራው ባለበት ቆመ::
“ጉድማን እዚህ ነው ያለኸው” የሚለው የሚክ ጆንሰን የቦስተን አይሪሽ ድምፅ በህንፃው ውስጥ አስተጋባ።
ይሄማ አይሆንም! እንዴት ይሄ ዘረጦ ድቡልቡል ሰው እዚህ ሊገኝ ቻለ? ብሎ ራሱን ጠየቀ፡፡
“ሉው የት ነው ያለኸው?”
ጉድማን ደሙ ቀዘቀዘበት። አሁን የሚፋለመው ከሁለት ሰዎች ጋር ነው
ማለት ነው፡፡ ከሮድሪጌዝ እና ከጆንሰን ጋር፡፡ ኒኪን ጆንሰን ከማግኘቱ በፊት
ማግኘት ይኖርበታል። አለበለዚያ ግን ሚክን መግደል ይኖርበታል፡፡ ያ ባይሆን ምርጫው ነው። አብረው በቆዩበት አንድ ዓመት ውስጥ ሚክ ጉድማንን እንደ አንድ ዘመዱ ነው የሚቆጥረው። አሁን ግን ነገሩ የሞት ሽረት ጉዳይ ነው፤ ለመጠራጠርም ሆነ ለሀዘኔታ ጊዜ የለውም፡፡
ወደ አሳንሰሩ መሮጥ ጀመረ፡፡
ምድር ውስጥ ተንበርክኮ እየዳኸ ያለው ሚክ ጆንሰን በእጁ ላይ ትንሽዬው የእጅ ባትሪው ሲወድቅ መራገም ጀመረ።
የተረገመ ጉድማን!”
ጆንስን የባልደረባውን መኪና ውጪ ላይ ካገኘ በኋላ ልክ እንደ ጉድማን የተከተለውን መንገድ ተከትሎ በቱቦው በኩል ነው ወደ ህንፃው ምድር ቤት
መድረስ የቻለው። ጉድማን እዚህ ድረስ መምጣት ችሏል። ይሄው የወለሉ
አቧራ ላይ የሚገኙት የእግሩ እና የእጁ ምልክቶች። ወለሉ ላይ “ጂ የሚል
ፊደል የተለጠፈበት የተሠራ መሀረብ ወድቆ አገኘ። መሀረቡ የጉድማን
መሆኑን ያወቀው ደግሞ የጉድማን ሥም የመጀመሪያው ፊደል ስለተፃፈበት
ነበር፡፡ አሁን በዚህ ዘመን ይሄ ሰው መሀረብ ይይዛል?” ብሎ ጆንስን
ተበሳጨበት፡፡ ሁሌም በጉድማን ነገሮች እንደተበሳጨ ነው። ለማንኛውም አሁን ጉድማን ከአበሳጭነት ወደ አደገኛነት ተሻግሯል። ስለዚህ ማንኛውንም አይነት መስዋዕትነት ከፍሎ ሊያስቆመው ይገባል።
ዶክተር ኒኪ ሮበርትስ እሱን በፍፁም ማመን አልነበረባትም። የጉድማን አለቃ ሉዊስ ሮድሪጌዝ ኒኪን ካልገደላት እና ይህቺን መልካም ዶክተር በህይወት ቢያገኛት ጆንስን ምን ማድረግ እንዳለበት ጠንቅቆ ያውቃል።
የእጅ መብራቱን አንስቶ የምድር ቤቱን ሲቃኝ የፊዩዙን ሳጥን ተመለከተ፡፡ ወድያውኑም የፊዩዙን ዋና ማብሪያና ማጥፍያ ወደ ላይ ሊመልስው መብራቱ ክፍሉን አጥለቀለቀው እና አይኑንን አጭበረበረው። ከላይ በኩል የሆነ ሰው ሲሮጥ ይሰማዋል፡፡
“ሉዊስ!” ብሎ ጮክ ብሎ ተጣራ፤ ድምፁም በህንፃው ውስጥ እያስተጋባ፡፡
የብረቱን መሰላል ይዞ ወደ ላይ መውጣት ጀመረ፡፡......
✨ይቀጥላል✨
ምድር ቤቱ የመጣበት እና ወደ ላይ ወደ ጠባቡ መንገድ የሚያወጣው ቱቦ
አለ። ከፊዩዝ ሳጥኑ ሃያ ጫማ ርቀት ላይ ደግሞ ከምድር ወደ ላይ የሚያወጣ የብረት ደረጃ (መሰላል) አለ፡፡
ጉድማን እየዳኸ ወደ መሰላሉ አመራ፡፡ ሁሉ ነገር ፀጥ ብሏል፡፡ መብራቱን ካጠፋ ከሰኮንዶች በኋላ የተኩስ ድምፅ ሰምቷል፤ ከዚያ በኋላ ግን ምንም ነገር ሊሰማ አልቻለም። ሉዊስ ሮድሪጌዝ ህንፃው ውስጥ ይሆን? ወይንስ ኒኪን ከገደላት በኋላ ህንፃውን ትቶ ወጥቶ ይሆን? “እንደዚያ ከሆነ ደግሞ ህንፃው ውስጥ ብቻዬን ነዋ የምገኘው?' ብሎ እያሰበ እያለ ከላይ ቀጭን የህመም ድምፅ ሰማ። “ኒኪ?” አለ እና ሽጉጡን ጨብጦ ወደ ላይ በመሰላሉ ላይ መውጣት ጀመረ፡፡
ሉዊስ ሮድሪጌዝ ልክ እንደ አዳኝ ተኩላ ፀጥ ብሎ ሲያዳምጥ ቆየ፡፡ አጠገቡ እንዳለች ይሰማዋል። ጥይቱ ስላቆሰላት ቶሎ ቶሎ ስትተነፍስ ይታወቀዋል፡፡
ሽጉጡን ጥብቅ አድርጎ እንደ ያዘ ድምፅ ወደሰማበት አቅጣጫ ተወረወረ፡፡ አንድ ጊዜ ካገኛት በኋላ አንገቷን አንቆ ጭንቅላቷን ወለሉ ላይ ይደፋዋል። ከዚያም ይሄንን የሚስቱን አኔን ልብ ሲመርዙበት የነበሩ ቃላትን ሲያወጣ የነበረ ጭንቅላቷን በጥይት ይበታትነዋል። በቃ ከዚያ በኋላ እሱ
እና አኔ በሰላም አብረው መኖር ይጀምራሉ።
“የት ነው ያለሺው?” ብሎም ወደ ፊት ተጠጋ። አሁን የትም ልታመልጠው አትችልም፡፡ ነገር ግን ወደ ፊት ሲጠጋ አየር እንጂ ምንም ነገር ሊያገኝ አልቻለም፡፡ 'የት አባቷ ነው የሄደችው?' አለ ለራሱ፡፡
ይሄኔም ሀይለኛ የሆነ ምት ከእግሮቼ መሀል ተሰማው፡፡ አዎን ድብን
ያለ ምት ቆለጡ ላይ ሲያርፍበት ህመሙ ከቁጥጥሩ በላይ ስለሆነበት ቆለጡን ታቅፎ ወደ ወለሉ ሸብረክ አለ። ከኋላውም ልክ አይጥ ወደ ጉድጓድ
ስትሮጥ የምታሰማው አይነት ድምፅ ተሰማው፡፡
'ወይኔ ይህቺ ሸርሙጣ በእግሬ ሥር ሾልካ አመለጠችኝ! አሁን በእርግጠኛነት ወደ ብረቶቹ ደረጃ ነው የምትሄደው! አለ ለራሱ፡፡
እንደምንም ብሎ ቀና አለና ጭለማው ውስጥ እየተኮሰ “እገድልሻለሁ!
እገድልሻለሁ!” እያለ ማጓራት ጀመረ፡፡
ተሳካልኝ! አመለጥኩኝ አለች ኒኪ ለራሷ፡፡
ኒኪ የተኩሶቹን ድምፅ የሰማቸው ለእሳት አደጋ መውጫ የተዘጋጀው ጫፍ ላይ ስትደርስ ነበር፡፡ ላይ ከደረሰች በኋላ በሩን ከፍታ በደረጃው ወደ ታች ወደ ምድር የሚያወርዳትን የብረት መሰላል ተመለከተች፡፡ ከታች ከውጪ በኩል የሚመጣ የምሽቱ ደብዘዝ ያለ ብርሃን ይታያታል። ታች ከወረደች በኋላ ቢያንስ የሆነ የሚረዳኝ ሰው አላጣም ብላ ኒኪ በተስፋ ተሞልታ መሰላሉን መውረድ ጀመረች፡፡ ከሁለት ደረጃዎች በኋላ ግን
በጥይት የተመታችው ቁስል ስቃይ ከመጠን በላይ ስለሆነባት የያዘችው
መስላል ከእጇ አምልጦ ወደ ታች ወረደ፡፡ “እግሬን” ብላ እየጮኸች ወደቀች፡፡
የመጀመሪያው ፎቅ ላይ ያለ ኮንክሪት ላይም አረፈች። ራሷን ለጥቂት
ሰኮንዶች ያህል ሳተችና ወደ ራሷ ተመለሰች። ወዲያውኑም ከኮንክሪቱ ጥግ ላይ ከሚገኝ አንድ ጓዳ መሰል ነገር ውስጥ እየተሳበች ገባች እና ጥቅልል
አለች።
ለአፍታ ያህል ከባድ ሀዘን ውስጧን ተሰማው፡፡ እምባዋም አይኗን ሞላው። አሁን ካለችበት ቦታ ሃያ ጫማ ያህል ወደ ታች የእሳት አደጋው መውጪያ በር ይታያታል፡፡ ለጥቂት ለማምለጥ ችላ ነበር፡፡ አሁን አንዱንም ጡንቻዋን ማንቀሳቀስ አትችልም፡፡ ስለዚህ ሮድሪጌዝ መጥቶ ይገድላታል። ከእንግዲህ ይህ ያለችበት የህይወቷ የመጨረሻ ክፍል ይሆናል ማለት ነው።
እዚያው ጥቅልል እንዳለች አይኗን ጨፈነች፡፡ ወዲያውኑም ያልጠበቀችው አይነት ሙቀት መላ ሰውነቷን ይሞቃት ጀመር፡፡ የሆነ ደስ የሚል ስሜትም ተሰማት። ውስጧ የነበረው ሀዘንም ፍርሃቷን እና የቁስሏን ህመም አስከትሎ ከውስጧ ተንኖ ሲወጣ ይታወቃታል። በምትኩም ወፍራም የድካም ብርድ ልብሱን ጫነባት፡፡
ተኚ ኒኪ፡፡ መተኛት አለብሽ አለች ለራሷ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ጉድማን የመስላሉ ጫፍ ላይ ከደረሰ በኋላ ወደ ላይ ተስቦ ወለሉ ላይ ወጣ፡፡ ክፍሉ ውስጥ በሚገኙት ከሁለቱ የቆሽሹ መስኮቶች የሚገባው ብርሃን የምሽቱን ደብዛዛ ብርሃን ወደ ውስጥ ያስገባሉ፡፡ ምድር ቤቱ ከዚህ በጣም ጭለማ ስለነበረ ግን አይኑ ወዲያው ነበር የተላመደው:: እና ማግላይቱን አጠፋው። ክፍሉ ትልቅ እና ባዶ መሆኑን ሲመለከት በደንብ ተረጋጋ።
በመቀጠልም ወደ ላይኛው ፎቅ ወደሚያወጣ አሳንሰር እየተንቀሳቀሰ እያለ ከታች ከምድር ቤቱ የሚያውቀው ድምፅ ስሙን ሲጠራው ባለበት ቆመ::
“ጉድማን እዚህ ነው ያለኸው” የሚለው የሚክ ጆንሰን የቦስተን አይሪሽ ድምፅ በህንፃው ውስጥ አስተጋባ።
ይሄማ አይሆንም! እንዴት ይሄ ዘረጦ ድቡልቡል ሰው እዚህ ሊገኝ ቻለ? ብሎ ራሱን ጠየቀ፡፡
“ሉው የት ነው ያለኸው?”
ጉድማን ደሙ ቀዘቀዘበት። አሁን የሚፋለመው ከሁለት ሰዎች ጋር ነው
ማለት ነው፡፡ ከሮድሪጌዝ እና ከጆንሰን ጋር፡፡ ኒኪን ጆንሰን ከማግኘቱ በፊት
ማግኘት ይኖርበታል። አለበለዚያ ግን ሚክን መግደል ይኖርበታል፡፡ ያ ባይሆን ምርጫው ነው። አብረው በቆዩበት አንድ ዓመት ውስጥ ሚክ ጉድማንን እንደ አንድ ዘመዱ ነው የሚቆጥረው። አሁን ግን ነገሩ የሞት ሽረት ጉዳይ ነው፤ ለመጠራጠርም ሆነ ለሀዘኔታ ጊዜ የለውም፡፡
ወደ አሳንሰሩ መሮጥ ጀመረ፡፡
ምድር ውስጥ ተንበርክኮ እየዳኸ ያለው ሚክ ጆንሰን በእጁ ላይ ትንሽዬው የእጅ ባትሪው ሲወድቅ መራገም ጀመረ።
የተረገመ ጉድማን!”
ጆንስን የባልደረባውን መኪና ውጪ ላይ ካገኘ በኋላ ልክ እንደ ጉድማን የተከተለውን መንገድ ተከትሎ በቱቦው በኩል ነው ወደ ህንፃው ምድር ቤት
መድረስ የቻለው። ጉድማን እዚህ ድረስ መምጣት ችሏል። ይሄው የወለሉ
አቧራ ላይ የሚገኙት የእግሩ እና የእጁ ምልክቶች። ወለሉ ላይ “ጂ የሚል
ፊደል የተለጠፈበት የተሠራ መሀረብ ወድቆ አገኘ። መሀረቡ የጉድማን
መሆኑን ያወቀው ደግሞ የጉድማን ሥም የመጀመሪያው ፊደል ስለተፃፈበት
ነበር፡፡ አሁን በዚህ ዘመን ይሄ ሰው መሀረብ ይይዛል?” ብሎ ጆንስን
ተበሳጨበት፡፡ ሁሌም በጉድማን ነገሮች እንደተበሳጨ ነው። ለማንኛውም አሁን ጉድማን ከአበሳጭነት ወደ አደገኛነት ተሻግሯል። ስለዚህ ማንኛውንም አይነት መስዋዕትነት ከፍሎ ሊያስቆመው ይገባል።
ዶክተር ኒኪ ሮበርትስ እሱን በፍፁም ማመን አልነበረባትም። የጉድማን አለቃ ሉዊስ ሮድሪጌዝ ኒኪን ካልገደላት እና ይህቺን መልካም ዶክተር በህይወት ቢያገኛት ጆንስን ምን ማድረግ እንዳለበት ጠንቅቆ ያውቃል።
የእጅ መብራቱን አንስቶ የምድር ቤቱን ሲቃኝ የፊዩዙን ሳጥን ተመለከተ፡፡ ወድያውኑም የፊዩዙን ዋና ማብሪያና ማጥፍያ ወደ ላይ ሊመልስው መብራቱ ክፍሉን አጥለቀለቀው እና አይኑንን አጭበረበረው። ከላይ በኩል የሆነ ሰው ሲሮጥ ይሰማዋል፡፡
“ሉዊስ!” ብሎ ጮክ ብሎ ተጣራ፤ ድምፁም በህንፃው ውስጥ እያስተጋባ፡፡
የብረቱን መሰላል ይዞ ወደ ላይ መውጣት ጀመረ፡፡......
✨ይቀጥላል✨
👍3👎1
#የወድያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
...አንድ ሰዓት ገደማ ከፈጀው የኅብረተሰብ ኑሮ ክርክራችን በኋላ
ከየወዲያሽ ጋር በስውር ስለ ፈጸምነው ፍቅራዊ ግንኙነት ቦጨቅጨቅ አድርጌ
ገለጽኩለት። በአውራ ጣቱና በሌባ ጣቱ መካከል እያሽከረከረ ሲያፍተለትላት
የነበረችውን ወረቀት አሽቀንጥሮ ወረወራት። የሚናገረውን እጅግም ሳያሰላስል
“አንዳንድ ሰዎች መጥፎ ነገርን ለማቀድና ለመፈጸም ምንኛ ይቀናቸዋል?
ሕይወትን ከመገንባት ይልቅ መናድና መበታተን እንዴት ይከሠትላቸዋል? ሌሎችን እፍ ባለ ገደል ላይ መገፍተር ደስ ያሰኛቸዋል?» ብሎ ከፊት ለፊቱ ቆሞ የሚታይ ተናካሽ ሐሳብ የቆመ ይመስል አፈጠጠ፡፡ ቀላ ያለውን ዞማ ጸጉሩን በግራ እጁ ወደ ፊትና ወደ ኋላ ማሻሸት ጀመረ፡፡ ምን እንደሚያስብ ባላውቅም ተበሳጨ፡፡ ሐሳቤንም ሆነ መላ አስተያዬቴን ሳይቀበለኝ ቀረ። አድራጎቴ ሁሉ በተራ እንስሳዊ ባሕሪ የተፈጸመ ስሕተት ብቻ ሳይሆን ወንጀል መሆኑንም አስረዳኝ::
ጭንቀት አጥለቀለቀኝ። ተገናናንታ ለመናገርና ለመፀጫወት ተዝናንታ
የቆየችው ምላሴ እሳት ውስጥ እንደ ገባች ጅማት ተኮማተረች።
«ልጓም አልባ ሥጋዊ ፍላጎትህን ለማርካትና ቅንጣት የሕይወት ደስታ
ለመቅመስ ስትል የሌላዉን የሕይወት መስኖ መድፈንና ዙሪያው ገደል
እንዲሆንበት ማድረግ መጥፎ ጭካኔ ነው። ሆምጣጣ ኑሮ እንዲጠብቀውና
እንዲሠቃይ ማቀድም ሰዎች ከሚፈጽሟቸው ነውረኛ ድርጊቶች መካከል አንዱ ክፍል ነው::
ሌላዉን ወደ ምድረ ፋይድ አሽቀንጥረህ አንተ ሽቅብ መመንጠቅ እንደማይገባህ ማወቅ ነበረብህ፡፡ ለአንተ በቂና ትክክለኛ የመሰለህ ምክንያት ሁሉ ለሌላዉ ስሕተትና ከንቱ ነገር ሊሆን ይችላል። እንዴት ሕይወትን በአንዲት ጠባብ የሕሊና መስታወት ብቻ ትመለከታታለህ? የሕሊናህ መስታወት ሰፊና
ንጽሕ መሆን አለበት» ብሎ ግንባሩን ማሻሸት ጀመረ፡፡ ማባሪያው እንዳልደረሰ
ገባኝ…. እውነትም ቀጠለ፡፡ «ይህን በመፈፀምና በርኩሰት የተጠቀለለ ጥቅም በማነፍነፍሀ ወደእንተ የኑሮ ደረጃ ልታደርሳት አትችልም፡፡ በሌሎች ላይ
የተተበተብክና የተንጠለጠልክ ግንደቢስ ሐረግ እንጂ ጠንካራና ሥር ሰድዳ
የበቀለች ችፍርግ ታህል እንኳ አይደለህም፡፡ በአንድ የሕይወት ጀልባ ላይ ለመንሳፈፍ የጋራ ውሳኔ ቢኖራችሁ ኖሮ እኔም በሐሳብሀ በተስማማሁ ነበር። ነገር ግን አንተና ብጤዎችህ ሁሉ ከሥሯ መነጋግላችሁ ለማድረቅና አበስብሳችሁ
ለመጣል ያሰፈሰፋችሁ ስግብግቦች እንጂ ለሰብአዊ እኩልነት መሥዋዕት ለመሆን እጃችሁን የምታነሡ እንዳልሆናችሁ ዕውቅ ነው:: የዚህ ዐይነቱን የግድ የለሽነት ድርጊትማ አንድ ተራ ኣራዊትስ ይፈፅመው የለም እንዴ? ገና ለገና ትተናኮለኝ ይሆናል ወይም ለምግብነት ትጠቅመኝ ይሆናል በማለት ሌላዋን የዋህ እንስሳ የሚያበክት አራዊትስ መች ጠፋና? ... ብሎ ክፍሉ ውስጥ ከተንቆራጠጠ በኋላ ፈንጠር ብሎ ሌላ መቀመጫ ላይ ተቀመጠ። ቀኝ እግሩ ግራ እግሩ ላይ ተደርባ
ወደ ፊትና ወደ ኋላ ስትወዛወዝ የሱሪውም ጫፍ አብራ ትርገፈገፋለች። ነገር እየቆፈረ ነው፡፡ በመስኮት በኩል ገብቶ እንደ ውሃ አዙሪት እየተሽከረከረ
ከሚወጣው አየር በስተቀር ሌላውን ድምፅ ተፈጥሮ የገዘተችው ይመስል ቤቱ
ረጭ አለ።
የጉልላት ቁጣና የክፍሉ ውስጥ ደንዳና ጸጥታ ስሜቴን አደነዘዘው:: ዐይኖቹ ጨፈን ገለጥ ጨፈን ገለጥ እያሉ ይርገበገባሉ፡፡ የዐይኑ እንቅስቃሴ
ዝምታን ጥሶ አካባቢውን ተንቀሳቃሽ ድምፆ ሊነዛበት አይችልምና ክፍሉ አውሬ
የማይላወስበት ውድቀት መመስሉን ቀጠለ፡፡ ብስጭቱ እየባሰበት በመሄዱ
በውስጡ ሲፈራገጥ የቆየው ንዴት ከንፈሩን እንደ ገጠመ «ህ እ» አሠኝቶ ዝም አሠኘው። ዝም ብዬ ማዳመጥ ፀጥ ብዪ በሐሳብ በትር መደብደብ ስለ መሰለኝ በውስጤ ያለውን ምክንያትና ሐሳብ ሁሉ ዘክዝኬ ለማቅረብ ተነሣሁ:: «አይ እንግዲህስ ሳይበቃህ አልቀረም» ብዬ በመጀመር «ምስጢሬን ያንዶለዶልኩልህና ሐሳቤን ያካፈልኩህ እውነተኛ ጓደኝነት ጠንካራ የሕሊና ግንኙነት ድልድይ በመሆኑ ነው:: ብሳሳትም ባልሳሳትም ባጠፋም ባላጠፋም የአንተ ሐቀኛ አቋም
የእኔ የሕይወት ምስክር ነው:: ያሰብኩትንና የወጠንኩትን የቸገረኝንና
ያጋጠመኝን ሁሉ ካላወየሁህማ የጓደኝነታችን ጥልቅ ትርጉምና መሠረቱ ምንድን ነው ሳልንገዳገድና ፊት
ለፊቴ ሳይጨግግ ልራመድና ልመለከትበት የሚያስችለኝን የአስተያየት መላ በማቅረብ ወደ ተደላደለ አካባቢ አዝልቀኝ እንጂ፣ መሳሳቴንማ እኔም ራሴ ቀደም ብዬ ተረድቸዋለሁ! » በማለት ጨረስኩ።ትኩር ብሎ አይቶኝ አቀረቀረና፣
«ብሳሳትም ባልሳሳትም ማለት አትችልም። አዎ ጓደኝነት የሁለት
ሰዎች መገናኛ የሕሊና ጋብቻ ናት” ብሏል አንድ የፈረንሳይ ምሁር ብሉ ጀመረና፣ ሙሉ ልቦናህ ጭምር እንጂ ሥጋዊ አካልህ ብቻውን ዘላቂና ድርጁ
አያደርገውም፡፡
ያውም ይኸ የአንተ አድራጎት የሌሎችን ሕይወትና ኑሮ የማጥቆሪያና የማሰናከያ ግልጽ ዝሙት እንጂ የጋብቻን ጠርዝ እንኳ የሚነካ ኢምንት የታማኝነት ድርጊት አይደለም፡፡
«በአንተና በእኔ ዐይነት ኑሮ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ቁልቁል ወርዶ መኖር የሞት ያህል ያስፈራቸዋል። በሌሎች ትከሻ ላይ ቆመው ወደ ላይ መውጣት የሚጥማቸውን ያህል ወደ ታችኛው ኑሮና ዓለም መውረድ ግን እጅግ ስለሚመራቸው በኃይልና በግዴታ ካልተዘረጠጡ በቀር አይንበረከኩም፡፡
አይወርዱም፡፡»
“ምንም እንኳ የልብ ጓደኛዬ ብትሆን ለአካባቢህ ኅብረተሰብ መርዝ ሆነህ
የሌላውን ሕይወት ለማጨለም ስትጣጣር ላይም ሆነ ስሰማ ዝም አልልህም።አንድ ሰው 'ጓደኛዬ ነህ' ሲልህ ጠላቴ አይደለህም ማለቱ ነው:: ስለዚህም ከጠላት የሚለይበትን አብይ ቁም ነገር በሚገባ ማሳየት ይገባዋል» ብሎ ነገር ለማብላላት ተግ አለ፡፡ ውርጃብኙን ፈርቼ ዝም ኣልኩ። በቅሬታ ጉልበቱን መታ መታ አደረገና ያም ሆነ ይህ ጠላትህን ከማሞገስ ደካም ወዳጅህን ማሻሻልና ማረም ወደር የሌለው መልካም ተግባር ነው» ብሎ ከወንበሩ ላይ ተነሳ።
ቁጣውን በወንድማዊ ትህትናና ለዘብታ ለማቀዝቀዝና ለመግባባት በመፈለጌ ጥፋተኝነቴን በምታስረዳ ልም የጸጸት ፈገግታ ትክ ብዬ እያየሁ «መቼም በእኔ በኩል ያለው ነገር እንደ ከረመ እንቁላል በስብሷል። ከአንተ የምጠብቀው ደግሞ የቁጣ ቃላት ዶፍ ሳይሆን አራሚነት ያለው ተጨባጭ ድጋፍህን ነው» ብዬ ንግግሬን ሳልጨርስ ድጋፍ የምትጠይቀው አስነዋሪ ድርጊትህን የመደበቂያና ከማታመልጠው የሕሊና ፍርድ የማምለጫ ጥያቄ እንጂ እውነትን ለማፍረጥረጥ እና ለእርሷ እንደ ጸጉር የቀጠነችባትን የሕይወት ጐዳና
ለማስፋትና ለማደላደል አይደለም። እንደ ቀስተ ደመና አምረህ ለመጉበጥ እንጂ
መሰናክል እንዳላጋጠመው የብርሃን ጨረር ቀጥ ብለህ ለመጓዝ አይደለም» ብሎ ፊቱን አዙሮ ቆመ፡፡ «እኔ የምልህ እኮ፣ ዛሬ በምን ላይ ቆሜ ስለ ነገ በምን ሁኔታ መዘጋጀት እንደምችል ንገረኝ ነው:: በእኔ መዘዝ አስቸጋሪ ሕይውት
የሚያጋጥማትን ሰው በእጄ እየሳብኩ ወደ ትክክለኛ ዓለም የምትዘልቅበትን
መንገድና ዘዴ አሳየኝ ነው የምልህ» ብዬ በድፍረት መለስኩለት::
ድንገት ሳላስበው ፊቱን ወደ እኔ መለስ አደረገና የጊዜ ርዝመትም ሆነ እጥረት ያው ነው:: አንድን ተግባር ለማከናወን የሚፈጅብህን ጊዜ ማሳጠር ይቻላል፡፡ የአንዲት ደቂቃ የሕይወት ርዝማኔ ግን ምንጊዜም ቢሆን ያው ነው:: ትልቁ ግብግብ ያለው ካንተው ከራስህ ጋር ነው:: ሰው የለውጥ ምንጭ ነው፡ ነገ
ላይ ቆሜ፣ ዛሬ ላይ ተንበርክኬ ማለት የችግርህ ማቃለያ አይሆንም፡፡ ስንዘጋጅና
ዛሬ ነገ ስንል እፍኝ የማትሞላዋ ዕድሜያችን እንደ ማሰሻ ጨርቅ ነድዳ ነድዳ ታልቃለች ፡፡ የአንተ
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል
...አንድ ሰዓት ገደማ ከፈጀው የኅብረተሰብ ኑሮ ክርክራችን በኋላ
ከየወዲያሽ ጋር በስውር ስለ ፈጸምነው ፍቅራዊ ግንኙነት ቦጨቅጨቅ አድርጌ
ገለጽኩለት። በአውራ ጣቱና በሌባ ጣቱ መካከል እያሽከረከረ ሲያፍተለትላት
የነበረችውን ወረቀት አሽቀንጥሮ ወረወራት። የሚናገረውን እጅግም ሳያሰላስል
“አንዳንድ ሰዎች መጥፎ ነገርን ለማቀድና ለመፈጸም ምንኛ ይቀናቸዋል?
ሕይወትን ከመገንባት ይልቅ መናድና መበታተን እንዴት ይከሠትላቸዋል? ሌሎችን እፍ ባለ ገደል ላይ መገፍተር ደስ ያሰኛቸዋል?» ብሎ ከፊት ለፊቱ ቆሞ የሚታይ ተናካሽ ሐሳብ የቆመ ይመስል አፈጠጠ፡፡ ቀላ ያለውን ዞማ ጸጉሩን በግራ እጁ ወደ ፊትና ወደ ኋላ ማሻሸት ጀመረ፡፡ ምን እንደሚያስብ ባላውቅም ተበሳጨ፡፡ ሐሳቤንም ሆነ መላ አስተያዬቴን ሳይቀበለኝ ቀረ። አድራጎቴ ሁሉ በተራ እንስሳዊ ባሕሪ የተፈጸመ ስሕተት ብቻ ሳይሆን ወንጀል መሆኑንም አስረዳኝ::
ጭንቀት አጥለቀለቀኝ። ተገናናንታ ለመናገርና ለመፀጫወት ተዝናንታ
የቆየችው ምላሴ እሳት ውስጥ እንደ ገባች ጅማት ተኮማተረች።
«ልጓም አልባ ሥጋዊ ፍላጎትህን ለማርካትና ቅንጣት የሕይወት ደስታ
ለመቅመስ ስትል የሌላዉን የሕይወት መስኖ መድፈንና ዙሪያው ገደል
እንዲሆንበት ማድረግ መጥፎ ጭካኔ ነው። ሆምጣጣ ኑሮ እንዲጠብቀውና
እንዲሠቃይ ማቀድም ሰዎች ከሚፈጽሟቸው ነውረኛ ድርጊቶች መካከል አንዱ ክፍል ነው::
ሌላዉን ወደ ምድረ ፋይድ አሽቀንጥረህ አንተ ሽቅብ መመንጠቅ እንደማይገባህ ማወቅ ነበረብህ፡፡ ለአንተ በቂና ትክክለኛ የመሰለህ ምክንያት ሁሉ ለሌላዉ ስሕተትና ከንቱ ነገር ሊሆን ይችላል። እንዴት ሕይወትን በአንዲት ጠባብ የሕሊና መስታወት ብቻ ትመለከታታለህ? የሕሊናህ መስታወት ሰፊና
ንጽሕ መሆን አለበት» ብሎ ግንባሩን ማሻሸት ጀመረ፡፡ ማባሪያው እንዳልደረሰ
ገባኝ…. እውነትም ቀጠለ፡፡ «ይህን በመፈፀምና በርኩሰት የተጠቀለለ ጥቅም በማነፍነፍሀ ወደእንተ የኑሮ ደረጃ ልታደርሳት አትችልም፡፡ በሌሎች ላይ
የተተበተብክና የተንጠለጠልክ ግንደቢስ ሐረግ እንጂ ጠንካራና ሥር ሰድዳ
የበቀለች ችፍርግ ታህል እንኳ አይደለህም፡፡ በአንድ የሕይወት ጀልባ ላይ ለመንሳፈፍ የጋራ ውሳኔ ቢኖራችሁ ኖሮ እኔም በሐሳብሀ በተስማማሁ ነበር። ነገር ግን አንተና ብጤዎችህ ሁሉ ከሥሯ መነጋግላችሁ ለማድረቅና አበስብሳችሁ
ለመጣል ያሰፈሰፋችሁ ስግብግቦች እንጂ ለሰብአዊ እኩልነት መሥዋዕት ለመሆን እጃችሁን የምታነሡ እንዳልሆናችሁ ዕውቅ ነው:: የዚህ ዐይነቱን የግድ የለሽነት ድርጊትማ አንድ ተራ ኣራዊትስ ይፈፅመው የለም እንዴ? ገና ለገና ትተናኮለኝ ይሆናል ወይም ለምግብነት ትጠቅመኝ ይሆናል በማለት ሌላዋን የዋህ እንስሳ የሚያበክት አራዊትስ መች ጠፋና? ... ብሎ ክፍሉ ውስጥ ከተንቆራጠጠ በኋላ ፈንጠር ብሎ ሌላ መቀመጫ ላይ ተቀመጠ። ቀኝ እግሩ ግራ እግሩ ላይ ተደርባ
ወደ ፊትና ወደ ኋላ ስትወዛወዝ የሱሪውም ጫፍ አብራ ትርገፈገፋለች። ነገር እየቆፈረ ነው፡፡ በመስኮት በኩል ገብቶ እንደ ውሃ አዙሪት እየተሽከረከረ
ከሚወጣው አየር በስተቀር ሌላውን ድምፅ ተፈጥሮ የገዘተችው ይመስል ቤቱ
ረጭ አለ።
የጉልላት ቁጣና የክፍሉ ውስጥ ደንዳና ጸጥታ ስሜቴን አደነዘዘው:: ዐይኖቹ ጨፈን ገለጥ ጨፈን ገለጥ እያሉ ይርገበገባሉ፡፡ የዐይኑ እንቅስቃሴ
ዝምታን ጥሶ አካባቢውን ተንቀሳቃሽ ድምፆ ሊነዛበት አይችልምና ክፍሉ አውሬ
የማይላወስበት ውድቀት መመስሉን ቀጠለ፡፡ ብስጭቱ እየባሰበት በመሄዱ
በውስጡ ሲፈራገጥ የቆየው ንዴት ከንፈሩን እንደ ገጠመ «ህ እ» አሠኝቶ ዝም አሠኘው። ዝም ብዬ ማዳመጥ ፀጥ ብዪ በሐሳብ በትር መደብደብ ስለ መሰለኝ በውስጤ ያለውን ምክንያትና ሐሳብ ሁሉ ዘክዝኬ ለማቅረብ ተነሣሁ:: «አይ እንግዲህስ ሳይበቃህ አልቀረም» ብዬ በመጀመር «ምስጢሬን ያንዶለዶልኩልህና ሐሳቤን ያካፈልኩህ እውነተኛ ጓደኝነት ጠንካራ የሕሊና ግንኙነት ድልድይ በመሆኑ ነው:: ብሳሳትም ባልሳሳትም ባጠፋም ባላጠፋም የአንተ ሐቀኛ አቋም
የእኔ የሕይወት ምስክር ነው:: ያሰብኩትንና የወጠንኩትን የቸገረኝንና
ያጋጠመኝን ሁሉ ካላወየሁህማ የጓደኝነታችን ጥልቅ ትርጉምና መሠረቱ ምንድን ነው ሳልንገዳገድና ፊት
ለፊቴ ሳይጨግግ ልራመድና ልመለከትበት የሚያስችለኝን የአስተያየት መላ በማቅረብ ወደ ተደላደለ አካባቢ አዝልቀኝ እንጂ፣ መሳሳቴንማ እኔም ራሴ ቀደም ብዬ ተረድቸዋለሁ! » በማለት ጨረስኩ።ትኩር ብሎ አይቶኝ አቀረቀረና፣
«ብሳሳትም ባልሳሳትም ማለት አትችልም። አዎ ጓደኝነት የሁለት
ሰዎች መገናኛ የሕሊና ጋብቻ ናት” ብሏል አንድ የፈረንሳይ ምሁር ብሉ ጀመረና፣ ሙሉ ልቦናህ ጭምር እንጂ ሥጋዊ አካልህ ብቻውን ዘላቂና ድርጁ
አያደርገውም፡፡
ያውም ይኸ የአንተ አድራጎት የሌሎችን ሕይወትና ኑሮ የማጥቆሪያና የማሰናከያ ግልጽ ዝሙት እንጂ የጋብቻን ጠርዝ እንኳ የሚነካ ኢምንት የታማኝነት ድርጊት አይደለም፡፡
«በአንተና በእኔ ዐይነት ኑሮ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ቁልቁል ወርዶ መኖር የሞት ያህል ያስፈራቸዋል። በሌሎች ትከሻ ላይ ቆመው ወደ ላይ መውጣት የሚጥማቸውን ያህል ወደ ታችኛው ኑሮና ዓለም መውረድ ግን እጅግ ስለሚመራቸው በኃይልና በግዴታ ካልተዘረጠጡ በቀር አይንበረከኩም፡፡
አይወርዱም፡፡»
“ምንም እንኳ የልብ ጓደኛዬ ብትሆን ለአካባቢህ ኅብረተሰብ መርዝ ሆነህ
የሌላውን ሕይወት ለማጨለም ስትጣጣር ላይም ሆነ ስሰማ ዝም አልልህም።አንድ ሰው 'ጓደኛዬ ነህ' ሲልህ ጠላቴ አይደለህም ማለቱ ነው:: ስለዚህም ከጠላት የሚለይበትን አብይ ቁም ነገር በሚገባ ማሳየት ይገባዋል» ብሎ ነገር ለማብላላት ተግ አለ፡፡ ውርጃብኙን ፈርቼ ዝም ኣልኩ። በቅሬታ ጉልበቱን መታ መታ አደረገና ያም ሆነ ይህ ጠላትህን ከማሞገስ ደካም ወዳጅህን ማሻሻልና ማረም ወደር የሌለው መልካም ተግባር ነው» ብሎ ከወንበሩ ላይ ተነሳ።
ቁጣውን በወንድማዊ ትህትናና ለዘብታ ለማቀዝቀዝና ለመግባባት በመፈለጌ ጥፋተኝነቴን በምታስረዳ ልም የጸጸት ፈገግታ ትክ ብዬ እያየሁ «መቼም በእኔ በኩል ያለው ነገር እንደ ከረመ እንቁላል በስብሷል። ከአንተ የምጠብቀው ደግሞ የቁጣ ቃላት ዶፍ ሳይሆን አራሚነት ያለው ተጨባጭ ድጋፍህን ነው» ብዬ ንግግሬን ሳልጨርስ ድጋፍ የምትጠይቀው አስነዋሪ ድርጊትህን የመደበቂያና ከማታመልጠው የሕሊና ፍርድ የማምለጫ ጥያቄ እንጂ እውነትን ለማፍረጥረጥ እና ለእርሷ እንደ ጸጉር የቀጠነችባትን የሕይወት ጐዳና
ለማስፋትና ለማደላደል አይደለም። እንደ ቀስተ ደመና አምረህ ለመጉበጥ እንጂ
መሰናክል እንዳላጋጠመው የብርሃን ጨረር ቀጥ ብለህ ለመጓዝ አይደለም» ብሎ ፊቱን አዙሮ ቆመ፡፡ «እኔ የምልህ እኮ፣ ዛሬ በምን ላይ ቆሜ ስለ ነገ በምን ሁኔታ መዘጋጀት እንደምችል ንገረኝ ነው:: በእኔ መዘዝ አስቸጋሪ ሕይውት
የሚያጋጥማትን ሰው በእጄ እየሳብኩ ወደ ትክክለኛ ዓለም የምትዘልቅበትን
መንገድና ዘዴ አሳየኝ ነው የምልህ» ብዬ በድፍረት መለስኩለት::
ድንገት ሳላስበው ፊቱን ወደ እኔ መለስ አደረገና የጊዜ ርዝመትም ሆነ እጥረት ያው ነው:: አንድን ተግባር ለማከናወን የሚፈጅብህን ጊዜ ማሳጠር ይቻላል፡፡ የአንዲት ደቂቃ የሕይወት ርዝማኔ ግን ምንጊዜም ቢሆን ያው ነው:: ትልቁ ግብግብ ያለው ካንተው ከራስህ ጋር ነው:: ሰው የለውጥ ምንጭ ነው፡ ነገ
ላይ ቆሜ፣ ዛሬ ላይ ተንበርክኬ ማለት የችግርህ ማቃለያ አይሆንም፡፡ ስንዘጋጅና
ዛሬ ነገ ስንል እፍኝ የማትሞላዋ ዕድሜያችን እንደ ማሰሻ ጨርቅ ነድዳ ነድዳ ታልቃለች ፡፡ የአንተ
መስተካከያና መታነጫ ዛሬ እንጂ ነገማ የፍጻሜህ ዕለት ሊሆን ይችላል፡፡ ራስህን ድል ሳታደርግ በሌላው ላይ አትዝመት፡ በእድፍ ቅመም የተሰራ ሳሙና ሊያቆሽሽ እንጂ ሊያጸዳ አይችልም» ብሎ ጥቂት ዝም ካለ በኋላ «ሐሳብና እምነታቸውን ታውቀዋለህ፡፡ የወላጆችህ አጥንት፣ ሥጋ፣ ደም ክብርና ከንቱ ዝና ሁሉ ባንድ ጊዜ ተረስቶና ስንኩል እምነታቸው በመንፈቅና በዓመት ውስጥ ተለውጦ እሷን የሚቀበሉልህ ይመስልሃል? እንጃ! ይህ በትላንትና እና በዛሬው ትውልድ መካከል የይለይለት ሰይፍ የሚመዘዝበት የአመለካከት ጦርነት ነው» ብሎ ገረመመኝ፡፡
«እኔ መኖርና መግኘት የምፈልገው እኔን በሚመስለኝና በሚስማማኝ የአኗኗርና የሐሳብ አካባቢ እንጂ በእነርሱ የእምነት እና የአመለካከት ክልል አይደለም» ብዬ ከተቀመጥኩበት እስከምነሣ ካፌ ላይ ቀልቦ «አይሆንላቸውም እንጂ ቄሶች ሲሰብኩ ገነት ይቺ ናት፣ ሲኦል ያቺ ናት እያሉ በማሳየት ቢያስተምሩ እንዴት ደስ ባላቸው! ያሻህን ያህል ዕወቅ፣ ያስፈለገህን ያህል ምጠቅ፣ አንተን በልዩ ልዩ ሁኔታዎች የሚዳኝህ አካባቢህ ነው:: ለብቻህ ተነጥለህ ልትንሳፈፍ አይቻልህም አንተ በምትፈልገው ዓለም ውስጥ መኖር የምትችልበት ጊዜና ትውልድ ገና አልደረሰም:: ሕይወት የምትስተካከልበት ጊዜ ገና ነው።በጣም በጣም ሩቅ ነው። ያም ቢሆን የራሱ ሕግና የኑሮ ሥርዓት ይኖረዋል፡፡
ቀልድና ምር የየራሳቸው ጊዜና ቦታ አላቸው የወንዝ ዓመቴ ከምትንሳፈፍበት
ወንዝ ላይ ተነሥታ እስከምትበርበት ጊዜ ድረስ መላ አካሏን የምታሳርፈው
በውሃው ላይ ነው። የሕዝቡን ሕይወት ለመለወጥ የምትችለው በሕዝቡ ሕይወት
ውስጥ እየኖርክ ነው” ይባላል፡፡ የአንተም አስተሳሰብና የአኗኗር አመራር የሚመራውና የሚታዘዘው በአካባቢህና በውስጡ በሚገኙት የአብዛኛዎቹ ሰዎች
ትክክለኛ አስተሳሰብ እንጂ በዘፈቀደ የሚመራ ልዩ የኑሮ ደሴት ልትመሠርት
አትችልም። አንዲት ጠብታ ወለላ በአንድ ጋን መርዝ ውስጥ ምን ያህል ለውጥ
ታመጣ ይመስልሃል? ካልተመጣጠንክ ትወድቃለህ፡፡» ብሎ መጀመሪያ ወደ
ተቀመጠበት ቦታ ተመለሰ።
«ያበላሽሁትንና ያሰናከልኩትን ለማስተካከልና ለማቃናት ከቻልኩ ሙሉ
ሰው መሆኔን ዐውቃለሁ፡፡ በግድ የለሽነትም ያደናቀፍኳት ሕይወት የጸጸት ረመጥ ሆና ስታቃጥለኝና ስታሠቃየኝ እንድትኖር አልሻም፡፡
«ባስገደደኝ ችኩል ስሜት ተመርቼ የፈጸምኩትን በደል ሁሉ ለመደምሰስና ከእርሷ ጋር እስከ ዳር ለመዝለቅ ቃል እገባለሁ» ብዬ ሌላው የማቀርበው ሐሳብ ስለ ጠፋብኝ ዝም አልኩ፡፡
“ይህን መሰሉን ማኅበራዊ ችግር ብቻዬን አቃልላለሁ ብለህ አትወጠር፡፡
ማኅበራዊ ችግር የሚፈታው በሕዝብ ማኅበራዊ ትግል ነው :: የውሽት ባሕር ጤዛ የምታህል እውነት ሊሆን አይችልም። የአንድ ነገር ምስጢርና ይዞታ እስኪገለጽና እስኪታወቅ ድረስ ተለዋዋጭነት ያለው አይመስልም ይሆናል፡፡ ሰዎች ስንባል ሐሳባችንን ቆልምመን ስሜታችንን ለመግታት ያለን ጥንካሬ የተለያየ ነው፡፡ እንዲያውም የሐሳባቸው እስረኞችና ተገዢዎችም አሉ» ብሎ አፉን አባበሰ፡፡
«አንዲት ውብ አበባ እስከምትጠወልግ ድረስ እንኳ ረጋ ብለን በትዕግሥት
እናያትም፡፡ የመጀመሪያ አፍላ ውበቷ እንጂ በድርቀቷ ውስጥ የሚገኘው መልኳ
አይታየንም፡፡ አንተም እንዲሁ የዛሬውን የለጋነት ውበቷን ከአካባቢህ ተኩላዎች
ጋር ከተሻማህ በኋላ የሕይወቷ ዓዕም ብቻ ሲቀር በጥላቻ ተፍተህ ከፍላጐትህ
ውጭ ታደርጋታለህ ! » ብሉ ከግንባሩ እስከ አገጩ ድረስ ፊቱን ጠረገ፡፡
«ይህን ዐይነቱን ስሕተት በመፈጸም እኮ የመጀመሪያው ሰው እኔ አይደለሁም» ብዩ ጀመር ሳደርግ የመጀመሪያዉም የመጨረሻዉም አለመሆንህንና እንደማትሆንም አሳምሬ ዐውቃለሁ፡፡ በመጀመሪያ የሚያጋጥምነገርና እጅግም ልብ ሳይባልና ሳይታረም ያልፍ ይሆናል። የእያንዳንዱ ሰው ባህሪም የየራሱ መታወቂያና መለያ መሆኑን በሚገባ ዐውቃለሁ» ብሎ አንደ ፌንጣ ዘሎ
ጥሉኝ ወጣ፡፡
ፊት ለፊቴ ግዙፍ የሐሳብ ተራራ ስለ ተደነቀረ ወደ ፊትም ወደ ኋላም
መሄድና መንቀሳቀስ አቃተኝ ለመጀመሪያ ጊዜ ከራሴ ጋር የሐሳብ ትግልና ግብግብ ገጠምኩ።
ጌታነህ አልኩት ራሴን ከራሴ ጋር የማደርገውን ክርክርና ውጣ ውረድ
ስጀምር ቅንነቷንና ደጊቷን የወዲያነሽን እስከ መጨረሻዉ ለመሸከም አትችልም
ወይ? ጉልላት እንዳለው የሕይወቷን አፍላ ውበት በወረት ዐይን መግምገህ
ከልብህ ውስጥ ትተፋታለህ ወይ?” ብዬ ራሴን ጠየቅሁ፡፡ ሆኖም ጠቃሚ ነገር
እንደ ማሰብና እንደ መፈጸም አስቸጋሪ ነገር ስለሌለ ፈጣን ውሳኔ መስጠት
እያደር የሚንተገተግ እንጂ የሚጠፋ አለመሆኑን ስለማውቅ በልቤ ውስጥ
አቃተኝ፡፡ ራሴን የመፀየፍ ያህል ታዘብኩት። ከየወዲያነሽ ጋር ያለን ደማቅ ፍቅር የሚበራው ተስፋ ቀጠለ፡፡
ጉልላትም ቢሆን ይህን ጉዳይ እየዋለ እያደረ እንደሚረዳልኝ ጽኑነቴንም
ተመልክቶ እንደሚያበረታታኝ ዐውቅ ነበር፡፡ ጉልላት ፊቱን እንዳኮፋተረ ተመልሶ
ገባ።
ራሱን እየነቀነቀ ከተቀመጠ በኋላ «ተገዢነቷንና የበታችነቷን ምክንያት
በማድረግ የግዴታ ውዴታ ባስከተለው እሺታ ተጠቅመህ ለፈጸምከው በደል ምን ዓይነት ካሣ እንደምታቀርብ አላውቅም፡፡ እያንዳንዱ አእምሮ የየግሉ ዘዴ ይኖረዋል። እስከ መጨረሻው በእውነተኛ ቃልህ ተጠቅመህ ከጸናህም ሐቅን ለማግኘትና ውጤቷንም ለማየት እንደምትችል እርግጠኛ ነኝ፡፡ ግን የሕይወቷን ዳመራ ሳይሆን የሕይወቷን ዐመድ ለማየት የምትሻ ከሆንክ ሰው የመባያህ ቅመምና ትርጉም ሁሉ ከእለት ወደ እለት እየተፈቀፈቀ ይጠፋል። ነገም ከነገ ወዲያም የምታደርገውንና የምትፈጽመውን ሁሉ እየተከታተልኩ ሐሳቤንና ምክሬን አካፍልሃለሁ፡፡ ግን ወላዋይ መሆን የለብህም!» ብሎ ዝም አለ። ጉልላት ቀስ በቀስ ቀዘቀዘ፡፡ ሣቅና ጨዋታ ጀመርን፡፡ እንደተለመደው ቤቱን ፈገግታ አርከፈከፈበት። ከዚያ በኋላ ጠቅላላ ታሪኩን ከሥር መሠረቱ አንጠርጥሬ ነገርኩት።
ምንጊዜም ቢሆን በተለይ እሑድ እሑድ ከጉልላት ጋር ስለ ልዩ ልዩ ጉዳይ ቢያንስ ቢያንስ አንድ ሰዓት ያህል ክርክርና ውይይት ሳናደርጋ አንለያይም፡፡ ጉልላት ቁመቱ ዘለግ፣ ከወደ ትከሻው ሠፋ ብሎ ወደ ቅላቱ ወሰድሰድ ያደረገው ጸጉሩ ቀላ ያለ ዞማ ሲሆን ከወደ ግንባሩ ገለጥ ያለ ነው።ፊቱን ከግንባሩ የጀመሩ ወደ ታች ሲመለከቷት ሾጠጥ እያለች መጥበብ
የምታልቅ፡ የኻያ ስድስት ዓመት ወጣት ነው:: የንግድ ሥራ ኮሌጅ የሁለተኛ
ዓመት ተማሪ በነበረበት ጊዜ ትምህርቱን አቋርጦ ሥራ ጀመረ። ከአንድ ዓመት
ቆይታ በኋላ እንደገና የማታ ትምህርት ቀጠለ፡፡ «አብዛኛውን ጊዜ የሚመድቡኝ
ከሙያዩ ውጪ ነው:: የግብርና ሙያ የተማረውን የአናጢነት ሥራ ይሰጡታል።
ስለዚህ አመዳደባቸው ሁሉ ፍልስልሱ የወጣ ነው እያለ በመቃወም ከከራት
በማያንሱ የግል ሥራ ድርጅቶች ውስጥ እየተዘዋወረ ሠርቷል፡፡
አባቱ የሞቱት የ10 ዓመት ልጅ ሳለ ነበር። የነበራቸውን ሀብትና ንብረት ሁሉ ለእናቱ ለእርሱና ለእኅቱ በኑዛዜ አውርሰዋቸዋል። በከተማና በገጠር ያለው ንብረት ሁሉ መተዳደሪያቸው ነው፡፡ የሁለታችን ጓደኝነት ከልጅነታችን ጀምሮ የቆየና የደረጀ በመሆኑ እኔ ስለ እርሱ እርሱም ስለ እኔ ጠባይና ሁኔታ በሚገባ እናውቃለን፡፡ ምስጢረኞች ነን። የገንዘብም ይሁን የሌላ ጉዳይ ችግርና ሐሳብ ሲያጋጥመን በሙሉ ተስፋ ልቤን ሞልቼ የምሄደው ወደ ጉልላት ነው፡፡
አባቱ በሕይወት በነበሩበት ጊዜ በሠሩት ቤት ውስጥ እርሱና አንድ ፈት የሆነችው እኅቱ ከእናታቸው ጋር ይኖራሉ። የሚናገረውን ሐሳብ በቆራጥ ልቦና
ሥራ ላይ ለማዋልና ለመፈጸም በሚያደርገው መልካም ጥረትና ትዕግሥት ወለድ አፈጻጸም ከራሱ ይልቅ ሌሎችን ይጠቅማል፡፡
ቆንጆ
«እኔ መኖርና መግኘት የምፈልገው እኔን በሚመስለኝና በሚስማማኝ የአኗኗርና የሐሳብ አካባቢ እንጂ በእነርሱ የእምነት እና የአመለካከት ክልል አይደለም» ብዬ ከተቀመጥኩበት እስከምነሣ ካፌ ላይ ቀልቦ «አይሆንላቸውም እንጂ ቄሶች ሲሰብኩ ገነት ይቺ ናት፣ ሲኦል ያቺ ናት እያሉ በማሳየት ቢያስተምሩ እንዴት ደስ ባላቸው! ያሻህን ያህል ዕወቅ፣ ያስፈለገህን ያህል ምጠቅ፣ አንተን በልዩ ልዩ ሁኔታዎች የሚዳኝህ አካባቢህ ነው:: ለብቻህ ተነጥለህ ልትንሳፈፍ አይቻልህም አንተ በምትፈልገው ዓለም ውስጥ መኖር የምትችልበት ጊዜና ትውልድ ገና አልደረሰም:: ሕይወት የምትስተካከልበት ጊዜ ገና ነው።በጣም በጣም ሩቅ ነው። ያም ቢሆን የራሱ ሕግና የኑሮ ሥርዓት ይኖረዋል፡፡
ቀልድና ምር የየራሳቸው ጊዜና ቦታ አላቸው የወንዝ ዓመቴ ከምትንሳፈፍበት
ወንዝ ላይ ተነሥታ እስከምትበርበት ጊዜ ድረስ መላ አካሏን የምታሳርፈው
በውሃው ላይ ነው። የሕዝቡን ሕይወት ለመለወጥ የምትችለው በሕዝቡ ሕይወት
ውስጥ እየኖርክ ነው” ይባላል፡፡ የአንተም አስተሳሰብና የአኗኗር አመራር የሚመራውና የሚታዘዘው በአካባቢህና በውስጡ በሚገኙት የአብዛኛዎቹ ሰዎች
ትክክለኛ አስተሳሰብ እንጂ በዘፈቀደ የሚመራ ልዩ የኑሮ ደሴት ልትመሠርት
አትችልም። አንዲት ጠብታ ወለላ በአንድ ጋን መርዝ ውስጥ ምን ያህል ለውጥ
ታመጣ ይመስልሃል? ካልተመጣጠንክ ትወድቃለህ፡፡» ብሎ መጀመሪያ ወደ
ተቀመጠበት ቦታ ተመለሰ።
«ያበላሽሁትንና ያሰናከልኩትን ለማስተካከልና ለማቃናት ከቻልኩ ሙሉ
ሰው መሆኔን ዐውቃለሁ፡፡ በግድ የለሽነትም ያደናቀፍኳት ሕይወት የጸጸት ረመጥ ሆና ስታቃጥለኝና ስታሠቃየኝ እንድትኖር አልሻም፡፡
«ባስገደደኝ ችኩል ስሜት ተመርቼ የፈጸምኩትን በደል ሁሉ ለመደምሰስና ከእርሷ ጋር እስከ ዳር ለመዝለቅ ቃል እገባለሁ» ብዬ ሌላው የማቀርበው ሐሳብ ስለ ጠፋብኝ ዝም አልኩ፡፡
“ይህን መሰሉን ማኅበራዊ ችግር ብቻዬን አቃልላለሁ ብለህ አትወጠር፡፡
ማኅበራዊ ችግር የሚፈታው በሕዝብ ማኅበራዊ ትግል ነው :: የውሽት ባሕር ጤዛ የምታህል እውነት ሊሆን አይችልም። የአንድ ነገር ምስጢርና ይዞታ እስኪገለጽና እስኪታወቅ ድረስ ተለዋዋጭነት ያለው አይመስልም ይሆናል፡፡ ሰዎች ስንባል ሐሳባችንን ቆልምመን ስሜታችንን ለመግታት ያለን ጥንካሬ የተለያየ ነው፡፡ እንዲያውም የሐሳባቸው እስረኞችና ተገዢዎችም አሉ» ብሎ አፉን አባበሰ፡፡
«አንዲት ውብ አበባ እስከምትጠወልግ ድረስ እንኳ ረጋ ብለን በትዕግሥት
እናያትም፡፡ የመጀመሪያ አፍላ ውበቷ እንጂ በድርቀቷ ውስጥ የሚገኘው መልኳ
አይታየንም፡፡ አንተም እንዲሁ የዛሬውን የለጋነት ውበቷን ከአካባቢህ ተኩላዎች
ጋር ከተሻማህ በኋላ የሕይወቷ ዓዕም ብቻ ሲቀር በጥላቻ ተፍተህ ከፍላጐትህ
ውጭ ታደርጋታለህ ! » ብሉ ከግንባሩ እስከ አገጩ ድረስ ፊቱን ጠረገ፡፡
«ይህን ዐይነቱን ስሕተት በመፈጸም እኮ የመጀመሪያው ሰው እኔ አይደለሁም» ብዩ ጀመር ሳደርግ የመጀመሪያዉም የመጨረሻዉም አለመሆንህንና እንደማትሆንም አሳምሬ ዐውቃለሁ፡፡ በመጀመሪያ የሚያጋጥምነገርና እጅግም ልብ ሳይባልና ሳይታረም ያልፍ ይሆናል። የእያንዳንዱ ሰው ባህሪም የየራሱ መታወቂያና መለያ መሆኑን በሚገባ ዐውቃለሁ» ብሎ አንደ ፌንጣ ዘሎ
ጥሉኝ ወጣ፡፡
ፊት ለፊቴ ግዙፍ የሐሳብ ተራራ ስለ ተደነቀረ ወደ ፊትም ወደ ኋላም
መሄድና መንቀሳቀስ አቃተኝ ለመጀመሪያ ጊዜ ከራሴ ጋር የሐሳብ ትግልና ግብግብ ገጠምኩ።
ጌታነህ አልኩት ራሴን ከራሴ ጋር የማደርገውን ክርክርና ውጣ ውረድ
ስጀምር ቅንነቷንና ደጊቷን የወዲያነሽን እስከ መጨረሻዉ ለመሸከም አትችልም
ወይ? ጉልላት እንዳለው የሕይወቷን አፍላ ውበት በወረት ዐይን መግምገህ
ከልብህ ውስጥ ትተፋታለህ ወይ?” ብዬ ራሴን ጠየቅሁ፡፡ ሆኖም ጠቃሚ ነገር
እንደ ማሰብና እንደ መፈጸም አስቸጋሪ ነገር ስለሌለ ፈጣን ውሳኔ መስጠት
እያደር የሚንተገተግ እንጂ የሚጠፋ አለመሆኑን ስለማውቅ በልቤ ውስጥ
አቃተኝ፡፡ ራሴን የመፀየፍ ያህል ታዘብኩት። ከየወዲያነሽ ጋር ያለን ደማቅ ፍቅር የሚበራው ተስፋ ቀጠለ፡፡
ጉልላትም ቢሆን ይህን ጉዳይ እየዋለ እያደረ እንደሚረዳልኝ ጽኑነቴንም
ተመልክቶ እንደሚያበረታታኝ ዐውቅ ነበር፡፡ ጉልላት ፊቱን እንዳኮፋተረ ተመልሶ
ገባ።
ራሱን እየነቀነቀ ከተቀመጠ በኋላ «ተገዢነቷንና የበታችነቷን ምክንያት
በማድረግ የግዴታ ውዴታ ባስከተለው እሺታ ተጠቅመህ ለፈጸምከው በደል ምን ዓይነት ካሣ እንደምታቀርብ አላውቅም፡፡ እያንዳንዱ አእምሮ የየግሉ ዘዴ ይኖረዋል። እስከ መጨረሻው በእውነተኛ ቃልህ ተጠቅመህ ከጸናህም ሐቅን ለማግኘትና ውጤቷንም ለማየት እንደምትችል እርግጠኛ ነኝ፡፡ ግን የሕይወቷን ዳመራ ሳይሆን የሕይወቷን ዐመድ ለማየት የምትሻ ከሆንክ ሰው የመባያህ ቅመምና ትርጉም ሁሉ ከእለት ወደ እለት እየተፈቀፈቀ ይጠፋል። ነገም ከነገ ወዲያም የምታደርገውንና የምትፈጽመውን ሁሉ እየተከታተልኩ ሐሳቤንና ምክሬን አካፍልሃለሁ፡፡ ግን ወላዋይ መሆን የለብህም!» ብሎ ዝም አለ። ጉልላት ቀስ በቀስ ቀዘቀዘ፡፡ ሣቅና ጨዋታ ጀመርን፡፡ እንደተለመደው ቤቱን ፈገግታ አርከፈከፈበት። ከዚያ በኋላ ጠቅላላ ታሪኩን ከሥር መሠረቱ አንጠርጥሬ ነገርኩት።
ምንጊዜም ቢሆን በተለይ እሑድ እሑድ ከጉልላት ጋር ስለ ልዩ ልዩ ጉዳይ ቢያንስ ቢያንስ አንድ ሰዓት ያህል ክርክርና ውይይት ሳናደርጋ አንለያይም፡፡ ጉልላት ቁመቱ ዘለግ፣ ከወደ ትከሻው ሠፋ ብሎ ወደ ቅላቱ ወሰድሰድ ያደረገው ጸጉሩ ቀላ ያለ ዞማ ሲሆን ከወደ ግንባሩ ገለጥ ያለ ነው።ፊቱን ከግንባሩ የጀመሩ ወደ ታች ሲመለከቷት ሾጠጥ እያለች መጥበብ
የምታልቅ፡ የኻያ ስድስት ዓመት ወጣት ነው:: የንግድ ሥራ ኮሌጅ የሁለተኛ
ዓመት ተማሪ በነበረበት ጊዜ ትምህርቱን አቋርጦ ሥራ ጀመረ። ከአንድ ዓመት
ቆይታ በኋላ እንደገና የማታ ትምህርት ቀጠለ፡፡ «አብዛኛውን ጊዜ የሚመድቡኝ
ከሙያዩ ውጪ ነው:: የግብርና ሙያ የተማረውን የአናጢነት ሥራ ይሰጡታል።
ስለዚህ አመዳደባቸው ሁሉ ፍልስልሱ የወጣ ነው እያለ በመቃወም ከከራት
በማያንሱ የግል ሥራ ድርጅቶች ውስጥ እየተዘዋወረ ሠርቷል፡፡
አባቱ የሞቱት የ10 ዓመት ልጅ ሳለ ነበር። የነበራቸውን ሀብትና ንብረት ሁሉ ለእናቱ ለእርሱና ለእኅቱ በኑዛዜ አውርሰዋቸዋል። በከተማና በገጠር ያለው ንብረት ሁሉ መተዳደሪያቸው ነው፡፡ የሁለታችን ጓደኝነት ከልጅነታችን ጀምሮ የቆየና የደረጀ በመሆኑ እኔ ስለ እርሱ እርሱም ስለ እኔ ጠባይና ሁኔታ በሚገባ እናውቃለን፡፡ ምስጢረኞች ነን። የገንዘብም ይሁን የሌላ ጉዳይ ችግርና ሐሳብ ሲያጋጥመን በሙሉ ተስፋ ልቤን ሞልቼ የምሄደው ወደ ጉልላት ነው፡፡
አባቱ በሕይወት በነበሩበት ጊዜ በሠሩት ቤት ውስጥ እርሱና አንድ ፈት የሆነችው እኅቱ ከእናታቸው ጋር ይኖራሉ። የሚናገረውን ሐሳብ በቆራጥ ልቦና
ሥራ ላይ ለማዋልና ለመፈጸም በሚያደርገው መልካም ጥረትና ትዕግሥት ወለድ አፈጻጸም ከራሱ ይልቅ ሌሎችን ይጠቅማል፡፡
ቆንጆ
👍2
ሴት ባየ ቁጥር ከዐይኑ እስክትሰወር ድረስ የግልብጥሽ እያየ ባይኑ ይከተላታል፡፡ ለምን በዐይኑ እንደሚሸኝና ትክ ብሎ እንደሚመለከት ሲጠየቅ «ቆንጆ ማየት ኃጢአት እይደለም» የምትል ከባሕር ማዶ የመጣች ፈሊጥ አለችው::
ከንግድ ሥራ ነክ መጻሕፍት ሌላ ስለ ማኅበራዊ ኑሮ የተደረሱ መጻሕፍት መከታተል እጅግ ሲያስደስተው የታላላቅ ሰዎችን ታሪክና የትግል ሕይወት አዘውትሮ ማንበብ ያረካዋል። ካለፍ ካለፍ የወደዳቸው ሴቶች ዐልፎ ዐልፎ በሚያሳየው ሐሳበ ግትርነት የተነሣ ስሜታቸው እንደ ማለዳ አመዳይ ረግፎ
ይለዩታል። እርሱም በበኩሉ እንደ አማጭ እያዘገመ መፈላለጉን አይተውም፡፡
በተገናኘን ቁጥር ስለ እኔና ስለ የወዲያነሽ ፍቅር ስለምተርክለት ሐሳብ ለሐሳብ ተግባባን።
መጋቢት አቦ ካለፉ አራት ወሮች ተቆጠሩ፡፡ የየወዲያነሽ ውበት እንደ
ክረምት ጅረት በተፈጥሮ አሳላፊነት መሙላቱን ቀጠለ።
💫ይቀጥላል💫
ከንግድ ሥራ ነክ መጻሕፍት ሌላ ስለ ማኅበራዊ ኑሮ የተደረሱ መጻሕፍት መከታተል እጅግ ሲያስደስተው የታላላቅ ሰዎችን ታሪክና የትግል ሕይወት አዘውትሮ ማንበብ ያረካዋል። ካለፍ ካለፍ የወደዳቸው ሴቶች ዐልፎ ዐልፎ በሚያሳየው ሐሳበ ግትርነት የተነሣ ስሜታቸው እንደ ማለዳ አመዳይ ረግፎ
ይለዩታል። እርሱም በበኩሉ እንደ አማጭ እያዘገመ መፈላለጉን አይተውም፡፡
በተገናኘን ቁጥር ስለ እኔና ስለ የወዲያነሽ ፍቅር ስለምተርክለት ሐሳብ ለሐሳብ ተግባባን።
መጋቢት አቦ ካለፉ አራት ወሮች ተቆጠሩ፡፡ የየወዲያነሽ ውበት እንደ
ክረምት ጅረት በተፈጥሮ አሳላፊነት መሙላቱን ቀጠለ።
💫ይቀጥላል💫
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
...የብረቱን መሰላል ይዞ ወደ ላይ መውጣት ጀመረ፡፡
ሉዊስ ሮድሪጌዝ የኮሪደሩ መብራቶች በሙሉ ሲበሩ አይኑን ሽጉጥ በያዘበት እጁ ከለለ፡፡ ከታች ስሙ ሲጠራ ሰምቷል። የእነርሱን ጉዳይ የኒኪን ጉዲይ ከጨረሰ በኋላ ያስኬደዋል። አሁን ግን ኒኪን መግደል አለበት፡፡ እሷን የመግደሉ ሀሳብ በጣም አስደስቶታል። ከተቀመጠበት ተነስቶ ቆለጡ ላይ የሚሰማውን ህመም ችላ ብሎ ለእሳት አደጋ መውጫ ወደ ተሠራው የብረት ደረጃ አመራ።
እየመጣሁልሽ ነው አላት በዜማ ድምፅ እና ወደ ላይ ደረጃውን መውጣት ጀመረ። “የት ነው ያለሺው ነይ ወደ እዚህ!” እያለ ደረጃው ላይ የተንጠባጠበውን ጥቁር ደም እየተመለከተም ከደረጃው ጫፍ ላይ ከሚገኘው በር ላከ ደረሰ።
ሙሉ በሙሉ የበሩት የህንፃው መብራቶች ኒኪን ከእንቅልፏ አነቋት፡፡
ግን ተመልሳ ለዘላለም እንድታንቀላፋ ትደረጋለች፡፡ አዎን ልክ ዊሊ ባደንን
እንደገደለው እሷንም ያለችበት ቦታ ድረስ መጥቶ ሉዊስ ሮድሪጌዝ ይገድላታል። በቃ ከዚያ በኋላ ከባሏ ዶውግ ጋር ትገናኝ እና መልስ ላልተገኘላቸው ጥያቄዎቿ እራሱ መልስ ይሰጣታል። እውነታውንም
ታውቃለች ማለት ነው፡፡
“በጣም ነው የደከመኝ
ወደ ታች አይኗን ልካ በጥይት የተመታው እግሯን ተመለከተች፡፡ እንደ ቅድሙ ሀይለኛ ህመም አይሰማትም፡፡ ከዚያ ይልቅ ግን ቀዝቃዛ ውቅያኖስ
ውስጥ እንዳለች ሁሉ እግሯን በጣም ደንዝዟታል።
ከላይ በኩል ያለው የእሳት አደጋ መውጫ በር ተከፈተ እና የሮድሪጌዝን
ጭካኔ የተሞላበት የሹፈት ጥሪን ማዳመጥ ጀመረች።
“ዶክተርዬ የት ነሽ? እየመጣሁልሽ ነው እኮ” ይላታል፡፡
ፍርሃቷ ተመልሶ መጣባት፡፡ ከህመሟ የሚበልጠው ጥልቅ የመኖር ጉጉትም ውስጧን ተናነቃት፡፡ ስለሆነም ወደ ኋላ ወደ ጓዳው ግድግዳ እየተንፏቀቀች ተጠጋች እና ኮንክሪቱ ጋ ስትደርስ ተደግፋው ቁጭ አለች። ከተቀመጠችበት ቦታ ሆና በመጀመሪያ ጥቁሩን እና በደንብ ተደርጎ የተወለወለውን ጫማውን ተመለከተች፡፡ በመቀጠል ደግሞ እግሩን እና ሱሪውን፡ ከንፈሯም በፍርሃት የሆነ የልመና ድምፅ ሲያወጣ ይታወቃታል።
ይሄው አገኘሁሽ የኔ ውድ” አላት አጠገቧ እንደ ጅብራ ተገትሮ እንደቆመ፡፡ ሽጉጡን አዘቅዝቆ ይዞታል፡፡ ቀና ብለሽ ተመልከቺኝ” አላት፡፡ ኒኪም እንዳጎነበሰች ራሷን በአሉታ ነቀነቀች፡፡
ቀና ብለሽ እይኝ አንቺ ሸርሙጣ!” ብሎ ሲጮህባት ግን ኒኪ የግዷን ቀና
ብላ አየችው።
አቤት አይኖቹ! ውስጣቸው ያለው ጭካኔ ይታይባቸው ኖሮ እንዴት ያምሩ ነበር፡፡ ግን እነዚያ ቡናማ ውብ አይኖቹ ውስጥ የሚታዩት ጭካኔ ምህረት አልባነት እና ጥላቻ ስለሆነ ውበቱን አደብዝዞታል፡፡
ሽጉጡን ቀስ ብሎ ወደ እሷ ጭንቅላት አስጠግቶ በስስ ከንፈሮቹ ፈገግ
እያለ ተመለከታት።
“ሮድሪጌዝ መሳሪያህን ጣል ፖሊስ ነኝ
እንዳትተኩስባት!” የሚለው የጉድማን ድምፅ እንደ ህልም ሆኖ ይሰማት ጀመር፡፡
ሉዊስም ቢሆን ልክ እሷ የተሰማት አይነት ስሜት ነበር የተሰማው::
የሽጉጡን አፈሙዝ ግምባሯ ላይ ለጠፈው።
“ከኋላህ ነኝ ሉዊስ እንዳትተኩስባት” አለው፡፡
ኒኪም ጉድማን መሰላሉን ወርዶ ከሉዊስ ጀርባ ላይ ሽጉጡን እንዳነጣጠረ ተመለከተች፡፡ የደንብ ልብሱን ባይለብስም ሁሉ ነገሩ ግን በራስ
መተማመኑን እና ስልጣን ያለው መሆኑን ያሳያሉ። ግጥም ያለ መንጋጋው
እና ትዕዛዝ የሚሰጥበት ድምፁ ደግሞ ለዚያ ማሳያ ናቸው።
'የእኔ ህይወት ሊታደግልኝ ነው እዚህ ድረስ የመጣው! እና ጥልቅ የሆነ እፎይታ ሰውነቷን ወረራት።
ሮድሪጌዝም መሳሪያውን ወለሉ ላይ ጣላ እና ወደ ጉድማን ዞረ፡፡
ዘና ብሎ ጉድማንን ልክ በፊት እንደሚያውቀው ሰውም ያናግረው
ጀመር፡፡ “ፖሊስዬ አየህ አልገደልኳትም፡፡ ስለዚህ ለእሷ ያለህን ፍቅር ማሳየት ችለሃል” አለው እና ትንሽ ስቆ
“እሺ ከዚህ ቀጥሎስ ልታስረኝ ነው?” ብሎ ሁለቱን ክንዶቹን ወደ
ጉድማን ዘረጋ፡፡
ይሄ ሰውዬማ ዕብድ ነገር ነው፡፡ ብላ ኒኪ አሰበች። በቃ መጥፎ ብቻ ሳይሆን ዕብድ የአእዕምሮ ሆስፒታል ውስጥ ገብቶ ህክምና መከታተል የሚገባው ሰው ነው አለች በውስጧ፡፡
ጉድማንን ቀና ብላ እየተመለከተች በእስረኛው እጅ ላይ የእጅ ሰንሰለት
(ካቴና) ከማስገባቱ በፊት ለእስረኛው ስለመብቱ የሚናገረው ነገር ካለ ብላ
ጠበቀች፡፡ አዎን ሮድሪጌዝ ታስሮ ከአጠገቧ እስካልሄደ ድረስ ፍፁም ሰላም
አይሰማትም። መሳሪያ ባይዝ እንኳ በባዶ እጁ እንደሚጨርሳት..
ድው' የሚለው ብቸኛ የጥይት ድምፅ ተሰማት።
የሮድሪጌዝን ጭንቅላት አፈነዳው። የጭንቅላቱ የተበታተኑ አጥንቶች
እና አንጎሉም በብረት መሰላሉ ላይ፣ በኒኪ ልብስ ላይ፣ በኒኪ ፊት ላይ እና
እጆች ላይ ከደም ጋር ተቀላቅለው ተበታተኑ።
በዝግታ የጉድማንን ሬሳ ተሻግሮ ኒኪ ወደምትገኝበት ግድግዳ ተጠጋ እና
ለስላሳ እጁን ደም የነካውን ጉንጫ ላይ አሳረፈ።
“ልታስረው አልፈለግክም!”
“አዎን አልፈለግኩም!” ብሎ መለሰላት፡፡
ይሄኔም ኒኪ በሀይል መንቀጥቀጥ ጀመረች። በመቀጠልም በጣም
እየተንሰቀሰቀች አልቅሳ ተረጋጋች
“አመሰግናለሁ!” አለችው እና በሁለቱ እጆቿ አንገቱን አቅፋ ልጥፍ አለችበት።
ለጥቂት ጊዜ ያህል አቅፋው ከቆየች እና የደህንነት ስሜት ከተሰማት በኋላ ከእቅፉ ተላቅቃ ግድግዳውን ተደገፈች። እግሯ ሙሉ በሙሉ ደንዝዟል። ወደ ሆስፒታል በቶሎ መሄድ ይኖርባታል፡፡
“ህይወቴን ስላተረፍክልኝ እጅግ በጣም አመሰግናለሁ።” አለች እና በአይኗ አይኑን ፈለገችው፡፡
እሱም አይኑን መልሶ አይኗን ሲያያት ግን ለሰከንዶች ያህል ኒኪ ግራ ተጋባች:: አይኑ ውስጥ ቅድም ሮድሪጌዝ ሊገድላት ሲል ያየችውን ነገር ተመለከተች። ሰይጣንን፡፡
“በጣም የምትገርሚ ደደብ ሴት ነሽ” አላት እና ሽጉጡን ጭንቅላቷ ላይ
ደገነባት፡፡
ከዚያም ከፍተኛ ፍንዳታ ተሰማ እና ሁሉም ነገር ፀጥ አለ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ፊዮና ማክ ማን በጉድ ሰማርቲያን ሆስፒታል ውስጥ የምትሰራውን ስራ ትወደዋለች ፊዮና ነርስነትን እንደ ሥራ ሳይሆን እንደ የእጅ ሙያ ነው የምትቆጥረው፡፡ ማለትም ሌሎችን ለማገልገል በፈጣሪ ጥሪ እንደተደረገለት የቤተክርስቲያን አገልጋይ ነው የምታየው። “ጥሪያችንን ተከትለን በምንሥራው ሥራ አይደል እንዴ ገቢያችንን የምናገኘው?” እያለች እናቷ ጆኒ ትቀልድባታለች፡፡
እንደ ዕድል ሆኖ ደግሞ ሆስፒታሉ የሚከፍላት ክፍያ በጣም ጥሩ ነው።
በየቀኑ በጣም ጥሩ ሀኪሞች እና ነርሶች ጋር ነው የምትሰራው። በዚያ ላይ
ደግሞ የምታክማቸው ሰዎች የተለያዩ መሆናቸው ያዝናናታል። አንድ
አንዶቹ በጣም ህመም መቋቋም የሚችሉ ሰዎች ሲሆኑ፣ ሌሎች ደግሞ
ደጎች እና ሰዎችን አክባሪ ናቸው። አለ አይደል ለተደረገላቸው አገልግሎት
ምስጋናን የሚያቀርቡ ናቸው፡፡ በእርግጥ ሌሎችም አይነት ሰዎች አሉ::
የሚያመናጭቁ ሱሰኞች፣ በሽታቸው በጣም የሚያስቃያቸው ሰዎች ወይንም
ደግሞ ቁስላቸው እና በሽታቸው ሊታከምላቸው የማይችሉ ሰዎችም
ይገጥሟታል፡፡
ፊዮና የክፍሉን መጋረጃ ገልጣ ፀሐይ እንዲገባ ካደረገች በኋላ ዞር ብላ
አልጋው ላይ የተኛችውን ታካሚ ተመለከተቻት፡፡ እግሯ ላይ በጥይት
ተመታ እና ብዙ ደም ከፈሰሳት በኋላ ነው ወደዚህ ሆስፒታል ሌሊቱን ይዘዋት የመጡት፡፡ በጥሩ ሁኔታ የቀዶ ጥገና ከተደረገላቸውም በኋላ ቢሆን
አንድ አንድ በሽተኞች በጣም ሊጎዱ ወይንም ደግሞ ልባቸው ላይ ጉዳት
ሊደርስባቸው ይችላል፡፡ ወይንም ደግሞ ለሰዓታት፣ ለቀናት ወይም ደግሞ
ሳምንታት ያህል በደረሰባቸው አደጋ ሊሰቃዩ አዕምሮአቸው ሊረበሽ ይችላል
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
...የብረቱን መሰላል ይዞ ወደ ላይ መውጣት ጀመረ፡፡
ሉዊስ ሮድሪጌዝ የኮሪደሩ መብራቶች በሙሉ ሲበሩ አይኑን ሽጉጥ በያዘበት እጁ ከለለ፡፡ ከታች ስሙ ሲጠራ ሰምቷል። የእነርሱን ጉዳይ የኒኪን ጉዲይ ከጨረሰ በኋላ ያስኬደዋል። አሁን ግን ኒኪን መግደል አለበት፡፡ እሷን የመግደሉ ሀሳብ በጣም አስደስቶታል። ከተቀመጠበት ተነስቶ ቆለጡ ላይ የሚሰማውን ህመም ችላ ብሎ ለእሳት አደጋ መውጫ ወደ ተሠራው የብረት ደረጃ አመራ።
እየመጣሁልሽ ነው አላት በዜማ ድምፅ እና ወደ ላይ ደረጃውን መውጣት ጀመረ። “የት ነው ያለሺው ነይ ወደ እዚህ!” እያለ ደረጃው ላይ የተንጠባጠበውን ጥቁር ደም እየተመለከተም ከደረጃው ጫፍ ላይ ከሚገኘው በር ላከ ደረሰ።
ሙሉ በሙሉ የበሩት የህንፃው መብራቶች ኒኪን ከእንቅልፏ አነቋት፡፡
ግን ተመልሳ ለዘላለም እንድታንቀላፋ ትደረጋለች፡፡ አዎን ልክ ዊሊ ባደንን
እንደገደለው እሷንም ያለችበት ቦታ ድረስ መጥቶ ሉዊስ ሮድሪጌዝ ይገድላታል። በቃ ከዚያ በኋላ ከባሏ ዶውግ ጋር ትገናኝ እና መልስ ላልተገኘላቸው ጥያቄዎቿ እራሱ መልስ ይሰጣታል። እውነታውንም
ታውቃለች ማለት ነው፡፡
“በጣም ነው የደከመኝ
ወደ ታች አይኗን ልካ በጥይት የተመታው እግሯን ተመለከተች፡፡ እንደ ቅድሙ ሀይለኛ ህመም አይሰማትም፡፡ ከዚያ ይልቅ ግን ቀዝቃዛ ውቅያኖስ
ውስጥ እንዳለች ሁሉ እግሯን በጣም ደንዝዟታል።
ከላይ በኩል ያለው የእሳት አደጋ መውጫ በር ተከፈተ እና የሮድሪጌዝን
ጭካኔ የተሞላበት የሹፈት ጥሪን ማዳመጥ ጀመረች።
“ዶክተርዬ የት ነሽ? እየመጣሁልሽ ነው እኮ” ይላታል፡፡
ፍርሃቷ ተመልሶ መጣባት፡፡ ከህመሟ የሚበልጠው ጥልቅ የመኖር ጉጉትም ውስጧን ተናነቃት፡፡ ስለሆነም ወደ ኋላ ወደ ጓዳው ግድግዳ እየተንፏቀቀች ተጠጋች እና ኮንክሪቱ ጋ ስትደርስ ተደግፋው ቁጭ አለች። ከተቀመጠችበት ቦታ ሆና በመጀመሪያ ጥቁሩን እና በደንብ ተደርጎ የተወለወለውን ጫማውን ተመለከተች፡፡ በመቀጠል ደግሞ እግሩን እና ሱሪውን፡ ከንፈሯም በፍርሃት የሆነ የልመና ድምፅ ሲያወጣ ይታወቃታል።
ይሄው አገኘሁሽ የኔ ውድ” አላት አጠገቧ እንደ ጅብራ ተገትሮ እንደቆመ፡፡ ሽጉጡን አዘቅዝቆ ይዞታል፡፡ ቀና ብለሽ ተመልከቺኝ” አላት፡፡ ኒኪም እንዳጎነበሰች ራሷን በአሉታ ነቀነቀች፡፡
ቀና ብለሽ እይኝ አንቺ ሸርሙጣ!” ብሎ ሲጮህባት ግን ኒኪ የግዷን ቀና
ብላ አየችው።
አቤት አይኖቹ! ውስጣቸው ያለው ጭካኔ ይታይባቸው ኖሮ እንዴት ያምሩ ነበር፡፡ ግን እነዚያ ቡናማ ውብ አይኖቹ ውስጥ የሚታዩት ጭካኔ ምህረት አልባነት እና ጥላቻ ስለሆነ ውበቱን አደብዝዞታል፡፡
ሽጉጡን ቀስ ብሎ ወደ እሷ ጭንቅላት አስጠግቶ በስስ ከንፈሮቹ ፈገግ
እያለ ተመለከታት።
“ሮድሪጌዝ መሳሪያህን ጣል ፖሊስ ነኝ
እንዳትተኩስባት!” የሚለው የጉድማን ድምፅ እንደ ህልም ሆኖ ይሰማት ጀመር፡፡
ሉዊስም ቢሆን ልክ እሷ የተሰማት አይነት ስሜት ነበር የተሰማው::
የሽጉጡን አፈሙዝ ግምባሯ ላይ ለጠፈው።
“ከኋላህ ነኝ ሉዊስ እንዳትተኩስባት” አለው፡፡
ኒኪም ጉድማን መሰላሉን ወርዶ ከሉዊስ ጀርባ ላይ ሽጉጡን እንዳነጣጠረ ተመለከተች፡፡ የደንብ ልብሱን ባይለብስም ሁሉ ነገሩ ግን በራስ
መተማመኑን እና ስልጣን ያለው መሆኑን ያሳያሉ። ግጥም ያለ መንጋጋው
እና ትዕዛዝ የሚሰጥበት ድምፁ ደግሞ ለዚያ ማሳያ ናቸው።
'የእኔ ህይወት ሊታደግልኝ ነው እዚህ ድረስ የመጣው! እና ጥልቅ የሆነ እፎይታ ሰውነቷን ወረራት።
ሮድሪጌዝም መሳሪያውን ወለሉ ላይ ጣላ እና ወደ ጉድማን ዞረ፡፡
ዘና ብሎ ጉድማንን ልክ በፊት እንደሚያውቀው ሰውም ያናግረው
ጀመር፡፡ “ፖሊስዬ አየህ አልገደልኳትም፡፡ ስለዚህ ለእሷ ያለህን ፍቅር ማሳየት ችለሃል” አለው እና ትንሽ ስቆ
“እሺ ከዚህ ቀጥሎስ ልታስረኝ ነው?” ብሎ ሁለቱን ክንዶቹን ወደ
ጉድማን ዘረጋ፡፡
ይሄ ሰውዬማ ዕብድ ነገር ነው፡፡ ብላ ኒኪ አሰበች። በቃ መጥፎ ብቻ ሳይሆን ዕብድ የአእዕምሮ ሆስፒታል ውስጥ ገብቶ ህክምና መከታተል የሚገባው ሰው ነው አለች በውስጧ፡፡
ጉድማንን ቀና ብላ እየተመለከተች በእስረኛው እጅ ላይ የእጅ ሰንሰለት
(ካቴና) ከማስገባቱ በፊት ለእስረኛው ስለመብቱ የሚናገረው ነገር ካለ ብላ
ጠበቀች፡፡ አዎን ሮድሪጌዝ ታስሮ ከአጠገቧ እስካልሄደ ድረስ ፍፁም ሰላም
አይሰማትም። መሳሪያ ባይዝ እንኳ በባዶ እጁ እንደሚጨርሳት..
ድው' የሚለው ብቸኛ የጥይት ድምፅ ተሰማት።
የሮድሪጌዝን ጭንቅላት አፈነዳው። የጭንቅላቱ የተበታተኑ አጥንቶች
እና አንጎሉም በብረት መሰላሉ ላይ፣ በኒኪ ልብስ ላይ፣ በኒኪ ፊት ላይ እና
እጆች ላይ ከደም ጋር ተቀላቅለው ተበታተኑ።
በዝግታ የጉድማንን ሬሳ ተሻግሮ ኒኪ ወደምትገኝበት ግድግዳ ተጠጋ እና
ለስላሳ እጁን ደም የነካውን ጉንጫ ላይ አሳረፈ።
“ልታስረው አልፈለግክም!”
“አዎን አልፈለግኩም!” ብሎ መለሰላት፡፡
ይሄኔም ኒኪ በሀይል መንቀጥቀጥ ጀመረች። በመቀጠልም በጣም
እየተንሰቀሰቀች አልቅሳ ተረጋጋች
“አመሰግናለሁ!” አለችው እና በሁለቱ እጆቿ አንገቱን አቅፋ ልጥፍ አለችበት።
ለጥቂት ጊዜ ያህል አቅፋው ከቆየች እና የደህንነት ስሜት ከተሰማት በኋላ ከእቅፉ ተላቅቃ ግድግዳውን ተደገፈች። እግሯ ሙሉ በሙሉ ደንዝዟል። ወደ ሆስፒታል በቶሎ መሄድ ይኖርባታል፡፡
“ህይወቴን ስላተረፍክልኝ እጅግ በጣም አመሰግናለሁ።” አለች እና በአይኗ አይኑን ፈለገችው፡፡
እሱም አይኑን መልሶ አይኗን ሲያያት ግን ለሰከንዶች ያህል ኒኪ ግራ ተጋባች:: አይኑ ውስጥ ቅድም ሮድሪጌዝ ሊገድላት ሲል ያየችውን ነገር ተመለከተች። ሰይጣንን፡፡
“በጣም የምትገርሚ ደደብ ሴት ነሽ” አላት እና ሽጉጡን ጭንቅላቷ ላይ
ደገነባት፡፡
ከዚያም ከፍተኛ ፍንዳታ ተሰማ እና ሁሉም ነገር ፀጥ አለ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ፊዮና ማክ ማን በጉድ ሰማርቲያን ሆስፒታል ውስጥ የምትሰራውን ስራ ትወደዋለች ፊዮና ነርስነትን እንደ ሥራ ሳይሆን እንደ የእጅ ሙያ ነው የምትቆጥረው፡፡ ማለትም ሌሎችን ለማገልገል በፈጣሪ ጥሪ እንደተደረገለት የቤተክርስቲያን አገልጋይ ነው የምታየው። “ጥሪያችንን ተከትለን በምንሥራው ሥራ አይደል እንዴ ገቢያችንን የምናገኘው?” እያለች እናቷ ጆኒ ትቀልድባታለች፡፡
እንደ ዕድል ሆኖ ደግሞ ሆስፒታሉ የሚከፍላት ክፍያ በጣም ጥሩ ነው።
በየቀኑ በጣም ጥሩ ሀኪሞች እና ነርሶች ጋር ነው የምትሰራው። በዚያ ላይ
ደግሞ የምታክማቸው ሰዎች የተለያዩ መሆናቸው ያዝናናታል። አንድ
አንዶቹ በጣም ህመም መቋቋም የሚችሉ ሰዎች ሲሆኑ፣ ሌሎች ደግሞ
ደጎች እና ሰዎችን አክባሪ ናቸው። አለ አይደል ለተደረገላቸው አገልግሎት
ምስጋናን የሚያቀርቡ ናቸው፡፡ በእርግጥ ሌሎችም አይነት ሰዎች አሉ::
የሚያመናጭቁ ሱሰኞች፣ በሽታቸው በጣም የሚያስቃያቸው ሰዎች ወይንም
ደግሞ ቁስላቸው እና በሽታቸው ሊታከምላቸው የማይችሉ ሰዎችም
ይገጥሟታል፡፡
ፊዮና የክፍሉን መጋረጃ ገልጣ ፀሐይ እንዲገባ ካደረገች በኋላ ዞር ብላ
አልጋው ላይ የተኛችውን ታካሚ ተመለከተቻት፡፡ እግሯ ላይ በጥይት
ተመታ እና ብዙ ደም ከፈሰሳት በኋላ ነው ወደዚህ ሆስፒታል ሌሊቱን ይዘዋት የመጡት፡፡ በጥሩ ሁኔታ የቀዶ ጥገና ከተደረገላቸውም በኋላ ቢሆን
አንድ አንድ በሽተኞች በጣም ሊጎዱ ወይንም ደግሞ ልባቸው ላይ ጉዳት
ሊደርስባቸው ይችላል፡፡ ወይንም ደግሞ ለሰዓታት፣ ለቀናት ወይም ደግሞ
ሳምንታት ያህል በደረሰባቸው አደጋ ሊሰቃዩ አዕምሮአቸው ሊረበሽ ይችላል
👍3
ለማንኛውም አሁን አልጋ ላይ የምትገኘው በሽተኛ ፊት ገፅታ ጥሩ
ይመስላል። ደሟ ውስጥ ያለው የኦክሲጅን ደረጃም መልካም ይመስላል።
መስኮቱ ደፍ ላይ የሚገኙ አበቦችን እያስተካከለች ወደ ታች ስትመለከት
ከሆስፒታሉ ህንፃ መግቢያ በር ላይ ሪፖርተሮች፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኞችና
ቪዲዮ ቀራጮች እጅብ ብለው በመቀመጥ የበሽተኛዋን መንቃት በትጋት
እየጠበቁ ይገኛሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ፖሊሶች ኮሪደሩ ላይ ተቀምጠው
የበሽተኛዋን መንቃት ይጠብቃሉ፡፡ በሽተኛዋ ላይ አደጋ ከደረሰ 48 ሰዓት
ያለፉ ቢሆንም አሁንም ቢሆን የዜና ማሰራጫዎች ሁሉ የሚዘግቡት እዚህ
ክፍል ስለተኛችው ታካሚ ነው::
“ሄሎ”
የሚል ድምፅ ከበሽተኛዋ አልጋ አካባቢ የሰማችው ፊዮናም “ኦ በእግዚአብሔር ነቃሽ እንዴ! ቆይ ዶክተር ራይሌን ልጥራው::” አለቻትና ወደ በሩ
ስታመራ የበሽተኛዋ በጭንቀት የተሞላው ድምፅ ክፍሉ ውስጥ እንድትቆይ
አደረጋት፡፡
እዚህ መገኘት አይገባኝም ነበር፡፡ ለምንድነው እዚህ የተገኘሁት?” ብላ
ጠየቀቻት፡፡
“አይዞሽ ተረጋጊ። አንቺ የምትገኘው በጉድ ሰማርተያን ሆስፒታል ውስጥ ነው። እዚህ የመጣሺውም ከ” ብላ ፊዮና ተናግራ ሳትጨርስ “አይሆንም!” ብላ ኒኪ ጮኸችና “እኔ ሞቻለሁ!” ብላ ራሷን ትራሱ ላይ ወረወረችና ራሷን ሳተች። ወዲያውም የተገጠመላት ማሽን ድምፅ ያሰማ ጀመር። የልብ ምቷን የሚያሳየውን ማሽን ስክሪን ላይ የሚታየው ቁጥር
ወደ ታች መውረድ ጀመረ::
ይህንን ያየችው ፊዮናም በጣም ደንግጣ የክፍሉን በር ከፈተች፡፡ ኮሪደሩ
ላይ ሆና “ዶክተር ራይሌ እዚህ ክፍል በአስቸኳይ ይፈለጋል።” ብላ
ተጣራች፡፡
ዶክተር ሳም ራይሌ እየሮጠ የክፍሉን በር በርግዶ ገባ። ሳም ራይሌ በጉድ ሰማርተያን ሆስፒታል ውስጥ ምርጥ የቀዶ ጥገና ሀኪም ነው።
ይህችን ታካሚውን ደግሞ በደንብ አድርጎ ነው ቀዶ ጥገናውን የሰራላት። እናም የግድ በህይወት መቆየት አለባት።
“ምን አድርገሻት ነው?” ብሎም ፊዮናን እየወነጀለ ጥያቄውን ካቀረበላት
በኋላ የኒኪን የተከደኑ አይኖች በእጁ እየከፈተ ሲመለከታት ቆየ። አሁን
ማሽኑ የሚያሰማውን ድምፅ አቁሟል። የልቧ ምት ተስተካክሏል። ያም ሆኖ
ግን እነዚህ ድንገተኛ ራስን መሳቶች ጥሩ ምልክቶች አይደሉም።
“ኧረ እኔ ምንም አላደረግኳትም” አለች እና ፊዮና “የመስኮቱን መጋረጃ
ከከፈትኩኝ በኋላ እሷ አይኗን ከፈተች እና “ሄሎ” አለች በእርጋታ፤ ከዚያም ወዲያው ተለወጠች:: ከዚያም እኔ ሞቻለሁ፡፡ እዚህ መገኘት አይገባኝም እያለች ጮኸች እና ራሷን ሳተች፡፡” አለችው፡፡
ዶክተር ሳም ራይሌ የዶክተር ናኪ ሮበትስን ፊት በጥሞና ሲመለከት
ቆየ፡፡ ሳም ዶክተር ሮበርትስን በቴሌቪዥን ለብዙ ጊዜ አይቷታል።ምክንያቱም በዚህ “የዞምቢ ግድያ” የሚል ስያሜ በተሰጠው ርዕስ ላይ ዋነኛ የዜና ርዕስ ሆኖ ለሳምንታት ቆይታ ነበር፡፡ ምናልባትም ቆንጆ ስለ ሆነች ሊሆን ይችላል ብዙ ጊዜ የቴሌቪዥን ዜናዎች ስለ እሷ ሲዘግቡ የነበሩት።
ዶክተር ሳም ራይሌ ለዘጠኝ ሰዓታት ያህል በጥይት የተመታውን የእግሯን ሥጋ እና ጅማቶች ቀዶ ጥገና ሰርቷታል፡፡ ያም ሆኖ ግን ኢንፌክሽን ወይንም ደግሞ ከቀዶ ጥገናው በኋላ የልብ ምት ችግር
ሊያጋጥማት ይችላል።
“ሞርፊኑን ንቀይላት!” ብሎ ነርስ ማክ ማኑስን አዘዛት።
“የሞርፊኑን መጠን ቀንሺላት ማለትህ ነው?” ብላ ፊዮና በየዋህነት
ጠየቀችው፡፡
ሳምም አፍጥጦ እያያት “እኔ እንደዚያ ብዬሻለሁ?” ብሎ ሲቆጣት
“ኧረ አይደለም፡፡” ብላ ፊዮና ተደናበረች። ዶክተር ራይሌ እንደዚህ ቁጡ አልነበረም፡፡ ነገር ግን የዜና አውታሮች አትኩሮት ሁሉ እዚህ ክፍል የተኛችው ታካሚ ላይ ስለሆነ ጉዳዩ ጫና አሳድሮባቸዋል፡፡ “ግን እኮ ዶክተር
ራይሌ ሞርፊኑን ካቋረጥኩባት የቁስሉ ህመም በጣም ከፍተኛ ይሆንባታል::”
“መንቃት ይኖርባታል።” አላት እና የኒኪ ክንድ ደም ስሯ ላይ የተሰካውን ሞርፊን ነቅሎ ሳሊኑን ተከለላት “በዚያ ላይ ደግሞ” ብሎ የኒኪን የተቦጫጨረ ፊት ቁልቁል እያየ “ይህቺ ሴት አካላዊ ስቃይን በደንብ መቋቋም የምትችል ሴት ናት።” አላት፡፡
ዶክተር ራይሌ በእርግጥም ልክ ነበር፡፡ ኒኪ ከአንድ ሰዓት በኋላ ስትነቃ
የቀኝ እግሯ ላይ የሆነ ስው አሲድ እየጨመረባት እስኪመስላት ድረስ ነበር
በጣም ያቃጥላት የነበረው። ለነርሷም ይህንን ከፍተኛ ስቃይን
የሚያስወግድላትን ነገር እንድትሰጣት ለመነቻት፡፡
“ሀይለኛ የሞርፊን ኪኒንን ከኮዳይን ጋር ቀላቅዬ እሰጥሻለሁ።” አለቻት እና ፊዮና ይቅርታ በሚጠይቅ ድምፀትም “ዶክተር ራይሌ ሞርፊን አትስጪያት ብሎ ስላዘዘኝ ነው። ይቅርታ” አለቻት።
ኒኪም ፊቷን መልሳ ለነርሷ ጀርባዋን ሰጠቻት እና ዝም አለቻት፡፡ የቁስሉ ከፍተኛ ህመም በድጋሚ በህይወት እንደምትገኝ በደንብ አሳወቃት።
ይሄ ግን እንዴት ሊሆን እንደቻለ ግልፅ አልሆነላትም። እዚያ የመጋዘን ህንፃ
ውስጥ የሆነውን ነገር ስታስታውስ ጓደኛዋ እና የእሷን ህይወት ሊታደግ
መጋዘኑ ድረስ የመጣው ጉድማን የሽጉጡን አፈሙዝ ግንበሯ ላይ ደቅኖ
ሊተኩስባት ሲል ነበር፡፡
“በእውነት አንቺ አስገራሚ ደደብ ሴት ነሽ ብሏት አይደል? ደግሞም ልክ ነበር። ምክንያቱም ሉው ጉድማን ለምን ብሎ ነው የእሷን ሞት የሚፈልገው? እንደዚያ ከሆነ ታዲያ ለምንድን ነው ሊዊስ ሮድሪጌዝን የገደለው? ስለዚህ እሱ በዚያ ሰዓት እዚያ ቦታ ላይ የተገኘው ሊገድላት
አልነበረም ማለት ነው። ከዚያ በኋላ ህንፃው ውስጥ ስለተከሰቱት ነገሮች
ምንም አታስታውስም::
የህመሙ ማስታገሻ ኪኒኒዎችን ነርሷ ከፈረካከሰችላት በኋላ በምትወስደው የግሉኮስ ከረጢት ላይ ወጋቻት። ኒኪም የሚያቅለሸልሽ ስሜቷን ካባረረች በኋላ ነርሷን የተለያዩ ጥያቄዎችን ትጠይቃት ጀመር፡፡ነርሷ የመጋዘን ህንፃ ውስጥ ምን እንደተከሰተ እና እንዴትስ የኒኪ ህይወት
ሊተርፍ እንደቻለ ምንም የምታውቀው ነገር እንደሌለ አወቀች::
“አንቺ እግርሽን በጥይት ስለተመታሽ ነው በአምቡላንስ ተጭነሽ ወደ ዚህ የመጣሺው” የሚለውን መልስ ብቻ ነበር የመለሰችላት፡፡ ኒኪ ሆስፒታል
እንደደረሰች በቀጥታ ወደ ቀዶ ጥገና ተወስዳ በዶክተር ራይሌ ዘጠኝ ሰዓት
የፈጀ ቀዶ ጥገና ተደረገላት። ቀዶ ጥገናው በደንብ እንደተካሄደ እና ዶክተር
ራይሌም “ተስፋ ያለው ቀዶ ጥገና ነው” ብሎ እንደነገራት፣ በዚህም የእግሯ
ቁስል በቶሎ ሊድንላት እንደሚችል መረዳቷን ጭምር ገለጠችላት፡፡
“ለማንኛውም እሱ ራሱ ሲመጣ ይህንን ነገር ይነግርሻል፡፡” አለቻት እና
ፊዮና ፈገግ ካለች በኋላም “ አንቺ እንደነቃሽ ደውዬ አሳውቄዋለሁ፡፡ ሌላኛው
ያንቺን ደህንነት አጥብቆ የሚጠይቀው ሰው ደግሞ ውጪ ኮሪደሩ ላይ
እየጠበቀሽ ነው፡፡ የቀዶ ጥገና ክፍሉ ውስጥ ከገባሽበት ጊዜ ጀምሮ እስከ
አሁን ድረስ ከሆስፒታሉ አልተንቀሳቀሰም። በእውነት የተባረከ ሰው ነው” አለቻትና ፈገግ አለች፡፡ ኒኪም ቆንጅዬዋን ባለ ቀይ ፀጉሯን ነርስ
እየተመለከተች
“ማነው የእኔን መንቃት ኮሪደሩ ላይ ሆኖ እየጠበቀኝ ያለው?” ብላ ጠየቀቻት፡፡
“ፖሊሱ ነዋ!” ብላ ነርሷ ከመለሰች በኋላ “ወደዚህ እንድትመጪ ያደረገው ፖሊስ ነው፡፡ በአምቡላንስ ካንቺ ጋር አብሮ ነው የመጣው። ምስኪን ሰው ነው:: በጣም ስላንቺ እንደተጨነቀ ያስታውቃል፡፡” አለቻት።
ኒኪ የተለያዩ ነገሮችን ማሰብ ጀመረች፡፡ ጉድማን ነው ማለት ነው እዚህ
ይዞኝ የመጣው? ግን እሱ ሊገድላት አልነበር እንዴ? ወይስ ሽጉጡን
ጭንቅላቷ ላይ የደቀነባት ነገር ብዙ ደም ስለፈሰሳት ያየችው ቅዥት ነው?
ወይስ ነገሩ ሌላ ነው?
“ፖሊሱን አሁን ላገኘው እችላለሁ?”
“እንዴታ ትችያለሽ እንጂ!” ብላ ነርሷ ፈገግ
ይመስላል። ደሟ ውስጥ ያለው የኦክሲጅን ደረጃም መልካም ይመስላል።
መስኮቱ ደፍ ላይ የሚገኙ አበቦችን እያስተካከለች ወደ ታች ስትመለከት
ከሆስፒታሉ ህንፃ መግቢያ በር ላይ ሪፖርተሮች፣ የቴሌቪዥን ጋዜጠኞችና
ቪዲዮ ቀራጮች እጅብ ብለው በመቀመጥ የበሽተኛዋን መንቃት በትጋት
እየጠበቁ ይገኛሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ፖሊሶች ኮሪደሩ ላይ ተቀምጠው
የበሽተኛዋን መንቃት ይጠብቃሉ፡፡ በሽተኛዋ ላይ አደጋ ከደረሰ 48 ሰዓት
ያለፉ ቢሆንም አሁንም ቢሆን የዜና ማሰራጫዎች ሁሉ የሚዘግቡት እዚህ
ክፍል ስለተኛችው ታካሚ ነው::
“ሄሎ”
የሚል ድምፅ ከበሽተኛዋ አልጋ አካባቢ የሰማችው ፊዮናም “ኦ በእግዚአብሔር ነቃሽ እንዴ! ቆይ ዶክተር ራይሌን ልጥራው::” አለቻትና ወደ በሩ
ስታመራ የበሽተኛዋ በጭንቀት የተሞላው ድምፅ ክፍሉ ውስጥ እንድትቆይ
አደረጋት፡፡
እዚህ መገኘት አይገባኝም ነበር፡፡ ለምንድነው እዚህ የተገኘሁት?” ብላ
ጠየቀቻት፡፡
“አይዞሽ ተረጋጊ። አንቺ የምትገኘው በጉድ ሰማርተያን ሆስፒታል ውስጥ ነው። እዚህ የመጣሺውም ከ” ብላ ፊዮና ተናግራ ሳትጨርስ “አይሆንም!” ብላ ኒኪ ጮኸችና “እኔ ሞቻለሁ!” ብላ ራሷን ትራሱ ላይ ወረወረችና ራሷን ሳተች። ወዲያውም የተገጠመላት ማሽን ድምፅ ያሰማ ጀመር። የልብ ምቷን የሚያሳየውን ማሽን ስክሪን ላይ የሚታየው ቁጥር
ወደ ታች መውረድ ጀመረ::
ይህንን ያየችው ፊዮናም በጣም ደንግጣ የክፍሉን በር ከፈተች፡፡ ኮሪደሩ
ላይ ሆና “ዶክተር ራይሌ እዚህ ክፍል በአስቸኳይ ይፈለጋል።” ብላ
ተጣራች፡፡
ዶክተር ሳም ራይሌ እየሮጠ የክፍሉን በር በርግዶ ገባ። ሳም ራይሌ በጉድ ሰማርተያን ሆስፒታል ውስጥ ምርጥ የቀዶ ጥገና ሀኪም ነው።
ይህችን ታካሚውን ደግሞ በደንብ አድርጎ ነው ቀዶ ጥገናውን የሰራላት። እናም የግድ በህይወት መቆየት አለባት።
“ምን አድርገሻት ነው?” ብሎም ፊዮናን እየወነጀለ ጥያቄውን ካቀረበላት
በኋላ የኒኪን የተከደኑ አይኖች በእጁ እየከፈተ ሲመለከታት ቆየ። አሁን
ማሽኑ የሚያሰማውን ድምፅ አቁሟል። የልቧ ምት ተስተካክሏል። ያም ሆኖ
ግን እነዚህ ድንገተኛ ራስን መሳቶች ጥሩ ምልክቶች አይደሉም።
“ኧረ እኔ ምንም አላደረግኳትም” አለች እና ፊዮና “የመስኮቱን መጋረጃ
ከከፈትኩኝ በኋላ እሷ አይኗን ከፈተች እና “ሄሎ” አለች በእርጋታ፤ ከዚያም ወዲያው ተለወጠች:: ከዚያም እኔ ሞቻለሁ፡፡ እዚህ መገኘት አይገባኝም እያለች ጮኸች እና ራሷን ሳተች፡፡” አለችው፡፡
ዶክተር ሳም ራይሌ የዶክተር ናኪ ሮበትስን ፊት በጥሞና ሲመለከት
ቆየ፡፡ ሳም ዶክተር ሮበርትስን በቴሌቪዥን ለብዙ ጊዜ አይቷታል።ምክንያቱም በዚህ “የዞምቢ ግድያ” የሚል ስያሜ በተሰጠው ርዕስ ላይ ዋነኛ የዜና ርዕስ ሆኖ ለሳምንታት ቆይታ ነበር፡፡ ምናልባትም ቆንጆ ስለ ሆነች ሊሆን ይችላል ብዙ ጊዜ የቴሌቪዥን ዜናዎች ስለ እሷ ሲዘግቡ የነበሩት።
ዶክተር ሳም ራይሌ ለዘጠኝ ሰዓታት ያህል በጥይት የተመታውን የእግሯን ሥጋ እና ጅማቶች ቀዶ ጥገና ሰርቷታል፡፡ ያም ሆኖ ግን ኢንፌክሽን ወይንም ደግሞ ከቀዶ ጥገናው በኋላ የልብ ምት ችግር
ሊያጋጥማት ይችላል።
“ሞርፊኑን ንቀይላት!” ብሎ ነርስ ማክ ማኑስን አዘዛት።
“የሞርፊኑን መጠን ቀንሺላት ማለትህ ነው?” ብላ ፊዮና በየዋህነት
ጠየቀችው፡፡
ሳምም አፍጥጦ እያያት “እኔ እንደዚያ ብዬሻለሁ?” ብሎ ሲቆጣት
“ኧረ አይደለም፡፡” ብላ ፊዮና ተደናበረች። ዶክተር ራይሌ እንደዚህ ቁጡ አልነበረም፡፡ ነገር ግን የዜና አውታሮች አትኩሮት ሁሉ እዚህ ክፍል የተኛችው ታካሚ ላይ ስለሆነ ጉዳዩ ጫና አሳድሮባቸዋል፡፡ “ግን እኮ ዶክተር
ራይሌ ሞርፊኑን ካቋረጥኩባት የቁስሉ ህመም በጣም ከፍተኛ ይሆንባታል::”
“መንቃት ይኖርባታል።” አላት እና የኒኪ ክንድ ደም ስሯ ላይ የተሰካውን ሞርፊን ነቅሎ ሳሊኑን ተከለላት “በዚያ ላይ ደግሞ” ብሎ የኒኪን የተቦጫጨረ ፊት ቁልቁል እያየ “ይህቺ ሴት አካላዊ ስቃይን በደንብ መቋቋም የምትችል ሴት ናት።” አላት፡፡
ዶክተር ራይሌ በእርግጥም ልክ ነበር፡፡ ኒኪ ከአንድ ሰዓት በኋላ ስትነቃ
የቀኝ እግሯ ላይ የሆነ ስው አሲድ እየጨመረባት እስኪመስላት ድረስ ነበር
በጣም ያቃጥላት የነበረው። ለነርሷም ይህንን ከፍተኛ ስቃይን
የሚያስወግድላትን ነገር እንድትሰጣት ለመነቻት፡፡
“ሀይለኛ የሞርፊን ኪኒንን ከኮዳይን ጋር ቀላቅዬ እሰጥሻለሁ።” አለቻት እና ፊዮና ይቅርታ በሚጠይቅ ድምፀትም “ዶክተር ራይሌ ሞርፊን አትስጪያት ብሎ ስላዘዘኝ ነው። ይቅርታ” አለቻት።
ኒኪም ፊቷን መልሳ ለነርሷ ጀርባዋን ሰጠቻት እና ዝም አለቻት፡፡ የቁስሉ ከፍተኛ ህመም በድጋሚ በህይወት እንደምትገኝ በደንብ አሳወቃት።
ይሄ ግን እንዴት ሊሆን እንደቻለ ግልፅ አልሆነላትም። እዚያ የመጋዘን ህንፃ
ውስጥ የሆነውን ነገር ስታስታውስ ጓደኛዋ እና የእሷን ህይወት ሊታደግ
መጋዘኑ ድረስ የመጣው ጉድማን የሽጉጡን አፈሙዝ ግንበሯ ላይ ደቅኖ
ሊተኩስባት ሲል ነበር፡፡
“በእውነት አንቺ አስገራሚ ደደብ ሴት ነሽ ብሏት አይደል? ደግሞም ልክ ነበር። ምክንያቱም ሉው ጉድማን ለምን ብሎ ነው የእሷን ሞት የሚፈልገው? እንደዚያ ከሆነ ታዲያ ለምንድን ነው ሊዊስ ሮድሪጌዝን የገደለው? ስለዚህ እሱ በዚያ ሰዓት እዚያ ቦታ ላይ የተገኘው ሊገድላት
አልነበረም ማለት ነው። ከዚያ በኋላ ህንፃው ውስጥ ስለተከሰቱት ነገሮች
ምንም አታስታውስም::
የህመሙ ማስታገሻ ኪኒኒዎችን ነርሷ ከፈረካከሰችላት በኋላ በምትወስደው የግሉኮስ ከረጢት ላይ ወጋቻት። ኒኪም የሚያቅለሸልሽ ስሜቷን ካባረረች በኋላ ነርሷን የተለያዩ ጥያቄዎችን ትጠይቃት ጀመር፡፡ነርሷ የመጋዘን ህንፃ ውስጥ ምን እንደተከሰተ እና እንዴትስ የኒኪ ህይወት
ሊተርፍ እንደቻለ ምንም የምታውቀው ነገር እንደሌለ አወቀች::
“አንቺ እግርሽን በጥይት ስለተመታሽ ነው በአምቡላንስ ተጭነሽ ወደ ዚህ የመጣሺው” የሚለውን መልስ ብቻ ነበር የመለሰችላት፡፡ ኒኪ ሆስፒታል
እንደደረሰች በቀጥታ ወደ ቀዶ ጥገና ተወስዳ በዶክተር ራይሌ ዘጠኝ ሰዓት
የፈጀ ቀዶ ጥገና ተደረገላት። ቀዶ ጥገናው በደንብ እንደተካሄደ እና ዶክተር
ራይሌም “ተስፋ ያለው ቀዶ ጥገና ነው” ብሎ እንደነገራት፣ በዚህም የእግሯ
ቁስል በቶሎ ሊድንላት እንደሚችል መረዳቷን ጭምር ገለጠችላት፡፡
“ለማንኛውም እሱ ራሱ ሲመጣ ይህንን ነገር ይነግርሻል፡፡” አለቻት እና
ፊዮና ፈገግ ካለች በኋላም “ አንቺ እንደነቃሽ ደውዬ አሳውቄዋለሁ፡፡ ሌላኛው
ያንቺን ደህንነት አጥብቆ የሚጠይቀው ሰው ደግሞ ውጪ ኮሪደሩ ላይ
እየጠበቀሽ ነው፡፡ የቀዶ ጥገና ክፍሉ ውስጥ ከገባሽበት ጊዜ ጀምሮ እስከ
አሁን ድረስ ከሆስፒታሉ አልተንቀሳቀሰም። በእውነት የተባረከ ሰው ነው” አለቻትና ፈገግ አለች፡፡ ኒኪም ቆንጅዬዋን ባለ ቀይ ፀጉሯን ነርስ
እየተመለከተች
“ማነው የእኔን መንቃት ኮሪደሩ ላይ ሆኖ እየጠበቀኝ ያለው?” ብላ ጠየቀቻት፡፡
“ፖሊሱ ነዋ!” ብላ ነርሷ ከመለሰች በኋላ “ወደዚህ እንድትመጪ ያደረገው ፖሊስ ነው፡፡ በአምቡላንስ ካንቺ ጋር አብሮ ነው የመጣው። ምስኪን ሰው ነው:: በጣም ስላንቺ እንደተጨነቀ ያስታውቃል፡፡” አለቻት።
ኒኪ የተለያዩ ነገሮችን ማሰብ ጀመረች፡፡ ጉድማን ነው ማለት ነው እዚህ
ይዞኝ የመጣው? ግን እሱ ሊገድላት አልነበር እንዴ? ወይስ ሽጉጡን
ጭንቅላቷ ላይ የደቀነባት ነገር ብዙ ደም ስለፈሰሳት ያየችው ቅዥት ነው?
ወይስ ነገሩ ሌላ ነው?
“ፖሊሱን አሁን ላገኘው እችላለሁ?”
“እንዴታ ትችያለሽ እንጂ!” ብላ ነርሷ ፈገግ
👍2❤1
አለች እና “አንቺ የጤንነት ስሜት እስከተሰማሽ ድረስ ለእሱ ልታገኚው እንደፈለግሽ እነግረዋለሁ፡፡”
“ግን አብረሺው ትመጫለሽ አይደል?” ብላ ኒኪ ፊቷ ላይ ፍርሃት እየተነበበባት” ጠየቀቻት፡፡ “ምናልባት የሆነ ነገር ብፈልግ እንድታመጪልኝ ብዬ ነው” አለቻት
ፊዮናም ኒኪን እያሳየቻት ምናልባት ይህ የፍርሃት ስሜቷ የመጣባት ከዚህ በፊት በደረሰባት ስቃዮች የተነሳ ሊሆን ይችላል' ብላ አሰበች እና “ችግር የለውም አብሬሽ እሆናለሁ። ደግሞም ሰውዬው ካደከመሽ
እና ምቾትም ከነሳሽ ከዚህ ክፍል አስወጣልሻለሁ” አለቻትና ፖሊሱን
ልትጠራላት ወጣች።
ኒኪም አልጋዋ ላይ ተጋድማ ለዘላለም የጠበቀችው አይነት ስሜት
ተሰማት፡፡
“ጉድማንን ምን ብዬ ነው ልጠይቀው የምችለው?” ምናልባትም ሽጉጡን
ጭንቅላቷ ላይ ደቅኖ በመጨረሻ ላይ ስለተናገራት ነገር እንዲያብራራላት
ትጠይቀው ይሆናል። ለማንኛውም ለሁለተኛ ጊዜ ህይወቷን አትርፎላታል።
ነፍሷን ለማዳንም እዚህ ድረስ በአምቡላንስ አብሯት መጥቷል። መዳፏን
በፍርሃት እና በሚሰማት ከፍተኛ የስቃይ ስሜት ምክንያት እያላባት ነው::
እራሷን ለማረጋጋትም ክንዷን በጥፍሯ ወጋችው። ኮሪደሩ ላይ የነርሷ ድምፅ ይሰማታል። “ይሄው እዚህ ክፍል ውስጥ ነው የምትገኘው።” ብላው በሩን ከፍታ ገባች።
ነርሷን ተከትሎ ክፍሉ ውስጥ የገባው መርማሪ ፖሊስ ሚክ ጆንሰን ፊቱን በፈገግታ አብርቶ “ዶክተር ሮበርትስ እንኳን ከሞት ዓለም ወደ ሞት
ዓለም በሰላም መጣሽ!” አላት።.....
✨ይቀጥላል✨
“ግን አብረሺው ትመጫለሽ አይደል?” ብላ ኒኪ ፊቷ ላይ ፍርሃት እየተነበበባት” ጠየቀቻት፡፡ “ምናልባት የሆነ ነገር ብፈልግ እንድታመጪልኝ ብዬ ነው” አለቻት
ፊዮናም ኒኪን እያሳየቻት ምናልባት ይህ የፍርሃት ስሜቷ የመጣባት ከዚህ በፊት በደረሰባት ስቃዮች የተነሳ ሊሆን ይችላል' ብላ አሰበች እና “ችግር የለውም አብሬሽ እሆናለሁ። ደግሞም ሰውዬው ካደከመሽ
እና ምቾትም ከነሳሽ ከዚህ ክፍል አስወጣልሻለሁ” አለቻትና ፖሊሱን
ልትጠራላት ወጣች።
ኒኪም አልጋዋ ላይ ተጋድማ ለዘላለም የጠበቀችው አይነት ስሜት
ተሰማት፡፡
“ጉድማንን ምን ብዬ ነው ልጠይቀው የምችለው?” ምናልባትም ሽጉጡን
ጭንቅላቷ ላይ ደቅኖ በመጨረሻ ላይ ስለተናገራት ነገር እንዲያብራራላት
ትጠይቀው ይሆናል። ለማንኛውም ለሁለተኛ ጊዜ ህይወቷን አትርፎላታል።
ነፍሷን ለማዳንም እዚህ ድረስ በአምቡላንስ አብሯት መጥቷል። መዳፏን
በፍርሃት እና በሚሰማት ከፍተኛ የስቃይ ስሜት ምክንያት እያላባት ነው::
እራሷን ለማረጋጋትም ክንዷን በጥፍሯ ወጋችው። ኮሪደሩ ላይ የነርሷ ድምፅ ይሰማታል። “ይሄው እዚህ ክፍል ውስጥ ነው የምትገኘው።” ብላው በሩን ከፍታ ገባች።
ነርሷን ተከትሎ ክፍሉ ውስጥ የገባው መርማሪ ፖሊስ ሚክ ጆንሰን ፊቱን በፈገግታ አብርቶ “ዶክተር ሮበርትስ እንኳን ከሞት ዓለም ወደ ሞት
ዓለም በሰላም መጣሽ!” አላት።.....
✨ይቀጥላል✨