አትሮኖስ
286K subscribers
121 photos
3 videos
41 files
572 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
ዷዷታና ንዝረቷ ተለወጠ፡፡

ስሟን በማወቄ ብቻ የመነሻው ምክንያት ያልተከሠተልኝ ሥውር ግን ብሩህ የሕሊና ደስታ ተሰማኝ፡፡ መላ ሰውነቴ ልገልፀው በማልችል ስሜት ተፍነከነከ፡፡

ማንቆርቆሪያውንና በጐድጓዳ ሳህን ውስጥ የነበረውን እጣቢ ይዛ ወጣች
ተልካ ስትመጣም ይሁን ወይም ባጋጣሚ ጉዳይ ጋሽ ጌታነህ ብላ በአንቱታ ስትጠራኝ በአክብሮቷ ሳይሆን ከድምጿ ለዛ ጋር አንቱ በማለቷ ብቻ
በእጅጉ ወደድኳት፡፡ስለ ቤት ሠራተኞች ሥራ ምንም የማያውቀውና ደንታ የሌለው አባቴ እንኳ ሲወራ በሰማው ትጉህ ሠራተኝነቷና ታዛዥነቷ ተደስቶ አንድ ሁለቴ ያህል አመስግኗል እናቴም በበኩሏ ከዚያ ቀደም ለማንኛዋም ሠራተኛ አሳይታ የማታውቀውን ደግነትና ቀረቤታ አሳይታለች። እናቴ ቀደም ሲል ያረጁ
ቀሚሶችዋንና ልብሶችዋን የምትሰጠው ላንዳንድ ድሃ ጐረቤቶቻችንና ለሌሎች
'የድሃ ዘመዶቼ ለምትላቸው ነበር፡፡

ዛሬ ግን በመጀመሪያ ተመርጦ የሚሰጠው ለየወዲያነሽ ሆነ፡፡ ከነባሮቹ
ሠራተኞች ጋር ባንዳንድ በጋርዮሽ በሚሠሩ ሥራዎች ካልተገናኙ በስተቀር
በማንኛውም ጊዜ እንዳትጠጋቸው ብዙ ጊዜ በጥብቅ ተነግሯታል፡፡ ምንም እንኳ
ረቂቅ የሆነ የበታችነት ስሜት ውስጥ ውስጡን ቢያነክታትም አብዛኛውን ጊዜ
የምታወራውና የምታቧልተው ከየውብነሽ ጋር ሆነ። ጠባይ ለጠባይ በደንብ እስከ
መተዋወቅና እስከ መግባባት ደረሱ፡፡ በእሷና በየወዲያነሽ መካከል ያለው
ግንኙነት ከዕለት ወደ ዕለት ደራ፡፡ መላ ቤተሰባችን እንደ ወደዳትና እናቴም
እሷን እኮ እንደ ልጄ ነው የማያት፡ ትሕትናዋ ብቻ ይበቃል» እንዳለች ዘጠኝ
ወሯ እንደ ዘጠኝ ቀን ዐለፈ።

የየወዲያነሽ አካላዊ ቅርፅና እቋም እየተስተካከለ አማረ፡፡ የተፈጥሮ ውበቷና ቁንጅናዋ ከያደፈጡበት ፉካ ቀስ በቀስ እያዘገሙ ወጡ፡፡ ጉንፎቿ ሞላ ብለው በትንቡክቡ የወጣትነት ደምና ሥጋ ጠረቁ። ምርጊቱ ተገሽልጦ እንደ
ወደቀ ግድግዳ ፈጥጦ የነበረው አጥንቷ በሥጋ ተሞልቶ በመጠርቃቱ ማለፊያ
ወጣት ሆነች፡፡ ድፍርስና ስርግ የነበሩት ዐይኖቿ ቅላታቸው ተገፍፎ በመጥራቱ፡
እንደ ውድቅት የጨለማ ውስጥ ጧፍ ቦግ ብለው ወጡ፡፡

ከሁሉም በላይ ደስ የሚያሰኘውና የሚማርከው ግን ፈገግ ብላ ስትሥቅ
ጠይሙ ጉንጫ ላይ ጉድጎድ ብለው የሚሰረሞጡት ድምብሉቿ የውበቷ ልዩ
ምንጮች ናቸው:: ያ ያረጀ ሞረድ ይመስል የነበረው ክንዷ እንደ መዳመጫ ድንጋይ ለስልሶ ውብ ገላ ሆነ። የውብነሽ ሁለትና ሦስት ገዜ ያሀል ከልብሶቿ መኻል የማይሆኗትንና ያረጁባትን መራርጣ ስለሰጠቻት የእናቴን ቦርቃቃ
ቀሚሶች አውልቃ ጣለች።

እኅቴና የወዲያነሽ በቁመትና በአካል መጠን አይተናነሱም፡፡ በዕድሜም
ቢሆን በጣም ተቀራራቢ ናቸው:: አብረው ሲቀመጡም ሆነ አጥር ግቢው ውስጥ
ከወዲያ ወዲህ ሲሉ በጣም ያምርባቸዋል። የወዲያነሽና እኅቴ ሲጠራሩ «አንቺ ስለሚባባሉ ጓደኝነታቸው እያደር ጠበቀ። የአንዳንድ ተራ ጉዳዮችም ምስጢረኛች የወዲያነሽ የተጣለላትን ልብስ ለብሳ ከየትኛውም አቅጣጫ ብቅኸ ስትል በውበቷና በደም ግባቷ ልቤ ክፉኛ መደንገጥ ጀመረ። አንዳንድ ቀን ያንን ጥቁር ዞማ ጸጉሯን ባራትና ባምስት ኣቅጣጫ በቀጭኑ ጐንጉና ትለቀዋለች።
የአጐናገኑን ዘዴ በመውደድ ዓይን መከታተል ልብ ያላልኩት ተግባሬ ሆነ፡፡

ደረጃ ስትወጣም ይሁን ስትወርድ የአካላቷ ንቅናቄና አካሒዷ ፀጉሯን ከወዲያ ወዲህ ሲያዘናፍለው የንፋስ ሽውሽውታ እንደሚያንቀሳቅሰው እንደ ለመለመ የወይን ሐረግ ቀንበጥ ደስ ይላል።

አልጋዬን ለማንጠፍ መኝታ ቤቴ በገባች ቁጥር የተዝረከረኩና የተበታኑ
መጻሕፍትና ወረቀቶች ሰብስባ ስለምታስቀምጥልኝ የግሌ ሠራተኛ ትመስል ነበር፡፡ወይዘሮ የውብዳር ወደ ቤት በመጡ ቁጥር ስለ እርሷ ጠባይና ሁኔታ እንዲሁም ታማኝነት ሳይጠይቁና
እ ..ሀ” ሳይሉ አይሔዱም፡፡

ከየወዲያነሽ ሳይሆን ከእናቴ ምስጋና ለማግኘት ሲሉ «ኪዳነምሕረትን፣ አቤት! ዛሬስ በጣም አምሮብሻል፡፡ እኔም እኮ ብየሻለሁ፡ እየሽው አይደል! ትልቅ
ሰው ቤት መግባት እንዲህ ያሳምራል፡፡ ወደፊትም ጠባይሽን አሳምረሽ በዚሁ
ዓይነት ዘለቅሽ እሜቴም ሆኑ ጌቶች ጥለው እይጥሉሽም» እያሉ ይሸነግሏታል።

እሑድ ዕለት ማታ ከራት በኋላ እንግዳ መቀበያ ክፍል ውስጥ ተቀምጬ
መፅሐፍ ሳነብብ እናቴ ከወደ መኝታ ቤት መጥታ እንካ እስኪ ጌታነህ ዛሬ
ደግሞ ለዚች ለየወዲያነሽ የአራት ወር ደሞዜን ተቀብያለሁ አስብለህ አስፈርምና
ስጣት፡፡ ያለፈውን የአራት ወር ደሞዝዋን ግን እርስዎ ጋ ይሁንልኝ ብላ እኔውጋ
አስቀምጨላታለሁ» ብላ ኻያ ብር ሰጥታኝ ሔደች። ምንጊዜም ከኔ ዘንድ
የሚቀመጠውን የደረሰኙን ደብተር ለማምጣት ወደ መኝታ ቤቴ ገባሁ፡፡ ነገር ግን እንደገና መመለስ ስላልፈለግሁ እዚያው ተቀምጬ ቀረሁ፡፡ የድካሟን ዋጋ
ተጠራቅሞ በማግኘቷና እንደ ከዚያ ቀደሞቹ ሠራተኞች «ይህን ሰብረሻል ያን
አጥፍተሻል» ተብላ ደሞ ባለመቆረጡ በልቤ ዙሪያ ልዩ ደስታ ተግፈለፈሉ።
የውብነሽ ለነገ ተሠርቶ የሚቀርብ የሒሳብና የድርሰት ሥራ አለብኝ ብላ መኝታ ቤቷን ዘግታ ሥራ ከጀመረች ቆይታለች። ከአራት በማይበልጡ መስመሮች የአራት ወር ደሞዜ ደርሶኛል የሚል ሐተታ ከጻፍኩ በኋላ ከመኝታ ቤቴ በር ላይ ብቅ ብዩ በቀስታ "የወዲያነሽ" ብዬ ተጣራሁ፡፡ አረንጓዴ ሻሿን በአንገቷ ዙሪያ በልቡ ሸብ አድርጋና ጸጉሯን እንደ ለምድ ትልታይ በጆሮ ግንዷ አኳያ አንዠርጋ በመጠኑ ወደ ውስጥ ዘልቃ ቆመች፡፡ “ገባ በይ» ብዬ ስላዘዝኳት ሁለት አጫጭር ርምጃዎች ወደፊት ተጠጋች፡፡ «በይ እንግዲህ እዚች ላይ ፈርሚ» ብዩ የቀኝ እጅ ክንዷን ተንጠራርቼ ያዝኩ። የአካላቷ ትኩሳት በጣቶቼና በመዳፌ በኩል ተሻግሮ ወደ መላ ሰውነቴ በልዩ ስሜታዊ ፍጥነት ተሰራጨ።

ሰውነቴ ንዳዱ እንደ ተነሣበት ሰው ውስጥ ውስጡን ተንዘፈዘፈ። አውራ
ጣቷን ቀለም ቀብቼ ለማስፈረም ወደ እኔ ሳስጠጋት ሣቅ አመለጣትና ወደ ውጭ
እንዳይሰማ ኣፏን በግራ እጅዋ ኣፍና ተንከተከተች:: መነሸዋን ባላውቅም በመሳቋ ረካሁ እንጂ ቅር አላኝም። አስፈረምኳት፡፡ «መጻፍና ማንበብ ትችያለሽ እንዴ?”ብዬ ጠየቅኋት። ጠይም ፊቷ በፈገግታ ወገግ በማለቱ በመስከረም ወር ቡቃያ ላይ ብርሃኗን የፈነጠቀች የጧት ፀሐይ መሰለች።

ፈገግታዋ ሳይቀንስ ከንፈሯ ተከፈተ። የልቦናዋን እንጃ! አፏን ግን ዝምታ ገታው፡፡ ትንሽ ዘግየት ብላ ግን «ብቻ» ብላ ዝም አለች፡፡ ብቻ” በማለት
የገታችው ሐሳቧ ግን አንጎሌ ውስጥ አዲስ የሃሳብ ቦይ ቀደደ፡፡

ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ የወዲያነሽን አስተካክዬ ለማየት ምቹ ሥፍራና ጊዜ
በማግኘቴ በጣም ደስ አለኝ። ምንም እንኳ በዚያች ሰዓትና አካባቢ ሰው
አለመኖሩን አሳምሬ ባውቅም በፍርሃትና በጥርጣሬ ዙሪያውን ቃኘሁት። የውስጣዊ
ስሜቴ እሳተ ገሞራ ናጠኝ፡፡ አድፍጦ አይጥ ስትጠባበቅ እንደ ቆየች ድመት
ዘልዩ እንገቷ ላይ ተጠመጠምኩ፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ግን ከእንቅልፉ እንደ ባነነ ሰው ወደ ትክክለኛው የውነት ዓለም ስመለስ አልጋዬ ላይ በግንባሬ ተደፍቼ ነበር። ማንም አጠገቤ ኣልነበረም። የወዲያነሽ እንዴት እንደ ሄደችና እንዴት እንደ ለቀቅኳት አልታወቀኝም። አልጋው ጫፍ ላይ የነበረው ደመወዟ ተበትኖ አገኘሁት፡፡

ገንዘቡን እንደገና ቆጥሬ ኮት ኪሴ ውስጥ ከተትኩ፡፡ ቀደም ሲል በፈጸምኩት ድርጊት ውስጣዊ ኃፍረት ተሰማኝ፡፡ መጠኑን የሳተ አካላዊ የስሜት ጥማት እንጂ አንዳችም እርካታ ሳላገኝ ቀረሁ፡፡ ልብሴን በማወላልቅበት ጊዜ
አቋቋሟና አነጋገሯ የዐይኖቿ ማራኪ ውበትና የአንገቷ አሰባበር በተለይም ከናፍሯ ከፊቴ መጥቶ ተደቀነ፡፡

በየዕለቱ ስለ እርሷ ማውጣትና ማውረድ መጨነቅና ማሰላሰል ጀመርኩ፡፡
አዲስ የሕይወት መስታወት
👍5
ከፊት ለፈታ ታየኝ! ጋደም እንዳልኩ «እኔና እሷ እኮ እኩል ነን፡ የሰው ልጅነት ሚዛናዊ እኩልነታችንና የተፈጥሮ ክብራችን
አይሳሳቅም፡፡ ከእንግዲህ ወዲህ እሷን እንደ በታቼና እንደ ተዋራጅ መቁጠር
የለብኝም» እያልኩ ልዩ ልዩ ምቶችንና በዐላማ ላይ የተመሠረቱ ተስፋዎችን
አንጎሌ ውስጥ ሸቅሽቄ ጥቂት ሰዓት አሳለፍኩ፡፡

በማግሥቱ ሰባት ሰዓት ተኩል ገደማ ላይ ለምሳ ወደ ቤት ስገባ ልብስ ስታጥብ ደረስኩ፡፡ መክረሚያዋን ቀና ብላ እንኳን አይታኝ አታውቅም ነበር፡፡እኔም እንደ ዘበት ነበር ኣልፌያት የምገባው:: በእጅዋ ላይ የነበረውን የሳሙና አረፋ እየፈነጠቀች ኃፍረት በሚያሳድዳት ፈገግታ አይታኝ ሥራዋን ቀጠለች፡፡
ምላሴ የተቋጠረች ወይም ከላንቃዬ ጋር የተሳከከች ይመስል «እንደምን ዋልሽ?»
ማለት እንኳ ተስኖኝ ዝም ብያት ገባሁ፡፡

አባቴና ሽምገልገል ያለ ሦስት አዛውንቶች ብዙ ወረቀቶች ዘርግተው ሲከራከሩና ሲጨቃጨቁ ደረስኩ፡፡ ጐንበስ ብዬ እጅ ነሣሁ፡፡ በትዕዛዝ የተነገሩ ይመስል ሁለም በአንድ ጊዜ ቀና ብለው አዩኝ፡፡ ከእንግዶች እንዱ ብቻ እንደምን ውለሃል» አሉኝ፡፡ ነገር እንደሚጎነጉኑና ጣለው ጠፍረው እንደሚሉ ስለ ገባኝ አንጎሌ እክ እንትፍ ብሏቸው በቀጥታ ወደ መኝታ ቤቴ ገብቼ በሩን ጎሰም አደረግሁት። የወዲያነሽ የእጅ ውሃ አምጥታ አስታጠበችኝ። ወጣ እንዳለች አካሌ
ልዩ ውስጣዊ እንቅስቃሴ ጀመረ። የልቤ እመታት ፍጥነት ተለወጠ።እያቁነጠነጠ
እንዳች የሚያንዘረዝር ነገር የተነሣብኝ ይመስል የሚያቅበጠብጥ ነገር ወረረኝ፡፡ ያመጣችልኝን እንጀራና ወጥ ባጠቧ ጠረጴዛ ላይ አስቀምጣልኝ ወጣች። ከእግር ጥፍሯ እስከ ራስ ጸጉሯ አየኋት፡፡ ለምን ወጥ እንዳላመጣችልኝ ባላውቅም እኔው እያወጣሁ በላሁ። በጥቂት ወራት ውስጥ ሰውነቷ እንዲህ በመለወጡ በጣም ተደነቅሁ። ደለል እንደ ተኛበት ቦይ ጉሮሮዬ እህል አላወርድ አለ። ጎንበስ ብላ መዓዱን በምታነበት ጊዜ “የውበት ቡቃያ አልኳት፡፡ በለሆሳስ ነበር። እጄን አስታጥባኝ ከወጣች በኋላ ልብሴን ቀያይሬ አለባበሴን በመስተዋት ተመለከትኩ፡፡ መኝታ ቤቴ ውስጥ የተንጠለጠለችው መስተዋት ቁመቷ አንድ ክንድ ተኩል ወርዷ እንድ ክንድ ይሆናል፡፡

አሁንም ወረቀታቸውን ዘርግተው በሚወያዩት ሰዎች አጠገብ ዐልፌ ወደ
ውጭ ወጣሁ፡፡ ወዲያም ወዲህ ሳልል የወዲያነሽ ልብስ ወደምታጥብበት ቦታ
ሄድኩ፡፡ . ያ ከልጅነቴ ጀምሮ የቦረቅሁበት፣ ኩኩሉና ኳስ የተጫወትኩበት ግቢ በጣም አስደሰተኝ፡፡

የምታጥበውን ልብስ እያየሁ «እማማና የውብነሽ ወዴት ሄዱ?» ብዬ ጠየቅኋት። የእነርሱን መኖርና አለመኖር የሚያስጠይቅ ምንም ምክንያት
አልነበረኝም፡፡ የመጠየቂያዬን ምክንያት እንጠርጥሬ ባላውቅም ወደ የወዲያነሽ
እያዳፋ የወሰደኝ በውስጤ የተቀጣጠለው የወጣትነት ነዲድ መሆኑ ገና እሷን ማነጋገር ስጀምር ገባኝ፡፡ ምንም እንኳ ባለፉት ወራት በልዩ ልዩ ጊዜ ዘና ብላ ስታወራ ብሰማትም አሁን ግን ልዩ ደስታ የሚሰጥ መስሎ ታየኝ።

«'አንቺም በዚያው ወደ ትምህርትሽ ትሄጃለሽ፡ ነይ አብረን እንሒድ
ብለው አሁን አንቱ ልትመጡ አቅራቢያ ወጣ አሉ» ብላ በሚገመጥ ፈገግታና
ሕይወት በሚያረሰርስ ሁናቴ እጅዋ አረፋው ውስጥ እንደ ተነከረ መለሰችልኝ፡፡
ምላሴ ተሳስራ እምቢ ባትለኝ ኖሮ ባያሌው ለማውራት አስቤ ነበር፡፡ ሆኖም
በኃፍረት ከተለጐመ ኣንደበት ጋር የሚደረግ ጊዜያዊ ግብግብ ከባድ በመሆኑ ዝምታዩ አይሎ ሰጥ አሰኘኝ፡፡ ደመወዟ ከእኔ ጋር ውሉ በማደሩ ከኪሴ አውጥቼ “እንቺ» አልኳት። ትኩር ብላ አይታ ተቀበለችኝ። ስንት እንደ ሰጠኋት እንኳ ሳትቆጥር በደረቷ በኩል ወደ ቀሚሷ ጉንፍ ለቀቀችው:: ከዚያም ቀጥ ብላ ስትቆም በእጅዋ ላይ የነበሩት የሳሙና አረፋዎች በፀሐይዋ ብርሃን የቀስተ ደመና ቀለማት ኀብር እያሳዩ ተራ በተራ ፈነዱ። በአእምሮዬ ውስጥ ወዲያው እየተረገዙና በሐሳብ ምጥ እየተወለዱ የሚፈነዱትን የፍቅር አረፋዎችና የመውደድ ትርኢቶች ግን በገሃድ ማየት አልቻልኩም፡፡ አይቼ ሳልጠግባት ተለያቻት ሄድኩ።

በሳምንቱ የውብነሽ ጋር ወደ ገበያ ወጥታ አዲስ ልብስ አሠፍታና ሌሎች ነገሮችም ገዝታ መጣች። ያ ውብ ጸጉሯ በአዲስ ቡናማ ሻሽ ሸብ ተደር ዘንከት ዘንነከት ስትል እንደ ማለዳ የአበባ ላይ ጤዛ የወጣትነት ዐይኔን ማረከችው። በእንግድነትም ይሁን በሌላ ጉዳይ ሰዎች ወደ ቤት መጥተ በሚያወሩበትና በሚጫወቱበት ጊዜ አንድ ዕቃ ለማቀበልም ይሁን ወይም

ነገር ለማቅረብ ስትመላለስ ሰዎች ባይናቸው እንኳ ሲከታተሏት ካየሁ ውስጤ በቅናት በግኖ አንጀቴ ያርር ነበር፡፡ አይተው የሚጨርሷት እንጂ እንደ ውብ
ኮከብ ከሩቁ ተመልክተው የሚተዋት ስለማይመስለኝ በንዴት እተክናለሁ። በባዶ የቅናት ስሜት እርር ድብን እያልኩ ቅናቴን ለመሰወር ያለማቋረጥ ተሠቃየሁ፡፡ በጣም ልዩ የሆነብኝ ግን የገዛ አባቴ እንኳ እያሞጋገሰ ሲጠራትና እንደ ስንዴ ቡቃያ ደስ እያለችው በአረጋዊ ፈገግታ ሲመለከታት በምሰማና በማይበት ጊዜ የቅናቴ ጥርቅም ቆመጡን ይዞ አናት አናቴን ይተረትረኛል። ዐይን
እንዳይጥልባት እና ምናልባትም ሁኔታው ከዚያ እንዳያልፍ ለማድረግ የምችልበትን ዘዴ ሌት ተቀን ማውጠንጠን ጀመርኩ። ለጊዜውም ቢሆን የአባቴ ዐይኖች በፍትወት ተነድፈው በሥጋዊ አምሮት ሳይጠመዱ አልቀሩም፡፡ ሆኖም
በምንም ይሁን በምን ከአባቴ ጋር ተሽቀዳድሜ እና ተፎካክሬ ድል ማድረግ
እንዳለብኝ ወዲያው ገባኝ፡፡ ፍቅራዊ ፍላጐቴን ከግቡ ለማድረስ ውስጣዊ
ብርታትና ከተደቆሰው ወኔዬ ውስጥ የተወለደው አዲሱ እልሄ በልዩ ኃይል
ወደፊት ገፋፋኝ። ጥንካሬው ገና ወደፊት ሊለይለት ነው፡፡
አንድ ቀን ማታ እንግዳ መቀበያ ክፍል ውስጥ እንደተሰበሰብን ቡና ተፈላ፡፡ የወዲያነሽ ቡና ለመስጠትና ስኒ ለመሰብሰብ ከወዲያ ወዲህ ትመላለስ
ነበር። የእኔና የአባቴ ዐይኖች የወዲያነሽ ዘንድ እየደረሱ ሲመለሱ ካንድም ሁለት
ሦስት ጊዜ ተጋጩ፡፡ በዚያች ሰዓት «ለምን ታያታለህ?» ብሎ ቢጠይቀኝ «አንተስ ለምን ታያታለህ?» ብዬ እመልስለታለሁ እያልኩ እኔዉ ከእኔው ጋር አተካራ ገጥሜ ተቀመጥኩ፡፡ በውስጤ ያልኩትን ሐሳብ ፊት ለፊት መናገር እንደማልችል ግን አሳምሬ ዐውቃለሁ፡፡

ቡናው ከተከተመ በኋላ ሒጂ እስኪ ከነ አስካለ ጋር ሆነሽ ያንን ጋን እጠኑት ብላ እናቴ ስላዘዘቻት የወዲያነሽ ወደ ምድር ቤት ወረደች።

የየወዲያሽን ከዚያ ግድም መሄድ ያወቀው አባቴ ታምቆ የከረመው
ስውር ፍላጐቱ ድንገት በመገንፈሉ ጉዳዩን አገላብጦ ሳያይ ውበቷን ገልጾ
ለመናገር ተገደደ።

ፊቱን በመጠነኛ ፈገግታ አፍክቶ ወደ እናቴ ዞር ካለ በኋላ «አንቺ ተካበች» አለ፡፡ እንደገና የምንትለኝ ይሆን የኃፍረት ገፅታ በፊቱ ላይ እየተነበበ።

«ይቺ ልጅ እንዴት አማረባት? ዘቢብ መሰለች አይደል እንዴ? እንዲህ ብስል ሎሚ የመሰለች ናትና!» ብሎ ንግግሩን ለመቀጠል አፉን እንደከፈተ፡ ያቺ ውስጥ ውስጡን በጥርጣሬ የተንሰዋለለችው እናቴን ቁጣዋን አዘጋጅታ የቆየች ይመስል“ያ በየሰው ቤት የምሰማውና ሆድ ሆዴን ሲበላኝ የኖረው ቅሌት ይባስ፧
ብሎ እዚሁ እቤቴ መጣ? 'አዛውንት ነኝ ልታፈር፡ ልከበር ማለት የለም፡፡ ቀሚስ ካጠለቀች፣ መቀነት ካዞረች አገባችበት መግባት ነው» ብላ ንዴት ስላዳፋት ዐይኖቿ ተጎለጎሉ፡፡ የሁለቱ ነገር እባብ ለእባብ ሆነብኝ፡፡ ቅፅበታዊ ቁጣዎ
እእምሮዋ ውስጥ ከተፀነሰ ነገር አፈትልኮ እንደወጣ ገባኝ። ለካስ ቀስ ብላ ትሰልል፣ ኖሯል አልኩ በውስጤ።....

💫ይቀጥላል💫
👍6
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_አርባ_አምስት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

....ቲናን አይኗን በፍርሃት ጎልጉላ እያየችው “ሚ/ር ዊሊያምስ እኔ ህይወቴን እፈልገዋለሁ። እንደ ድሮ ነፃ ሆኜ መኖር እፈልጋለሁ።” አለችው፡፡

አድሬኒ እንደነገረችው ከንቲባው ሴትየዋን በወሲብ የሚተነኩስበት አቋም የላትም። ባይሆን ቆንጆ እና ብልህ አዕምሮ እንዳላት ታስታውቃለች፡፡

“ብዙ ጊዜ ከቦታ ቦታ ቤት እየቀየርሽ ትዘዋወሪያለሽ?” ብሎ ጠየቃት፡፡
መልሷን ቢያውቀውም “አዎን። ምክንያቱም አንድ ቦታ ላይ ለብዙ ጊዜያት
መቆየት ለደህንነቴ ያሰጋኛል።” አለችው።

“ይሄ ደግሞ በጣም ወጪ ያበዛብሻል።” አላት እና በቀጥታ “ደንበኛዬ አንቺ ለምትሰጪኝ መረጃዎች በሙሉ ልትከፍልሽ ፈቃደኛ ናት” አላት፡፡

ቲና በእጇ ሀሳቡን አጣጣለችበት እና በመቀጠልም “አመሰግናለሁ ዴሪክ፡፡
ግን እውነቱን ስለተናገርኩ ብቻ ክፍያ መቀበሌ ምቾት አይሰጠኝም። አንተ
ጥሩ ሰው ትመስላለህ፡፡ ደምበኛህም ታማኝ ሳትሆን አትቀርም”
“ልክ ነሽ” አላት፡፡
“አንተ እንዳልከው እኛን አንድ አይነት ሰዎች የሚያስፈራሩን ከሆነ ከማን ጋር እየታገላችሁ እንደሆነ ጠንቅቃችሁ የምታውቁ አልመሰለኝም” አለችው፡፡

“ከሩሲያኖቹ ጋር ነው” አላት፡፡

ቲና ሥማቸውን እንኳን ገና ስትሰማ አይኗ በድንጋጤ ፈጠጠ፡፡

“አዎን” አላት በሹክሹክታ ድምፅ “ስለዚህ ደምበኛህን ከአካባቢው ዞር እንድትል ምከራት” ዊሊያም ስለ ኒኪ አሰበ እና ፈገግ ብሎ

“ይሄንን ያንቺን ምክር የምትቀበለው አይመስለኝም። እሷ በጣም ግትር
ሰው ናት” ብሎ መለሰላት፡፡

ይሄ እኮ ጨዋታ አይደለም” ብላ ቲና እየተቆጣች “ሰዎች እየሞቱ ነው፡፡
እኔ ያናገርኩት የኤልኤታይምስ ጋዜጣ ሪፖርተር እንኳን ሞቷል

”ዊሊያምስ ማስታወሻውን መውሰድ ጀመረ፡፡

“እነርሱ በልብ በሽታ ነው የሞተው ይላሉ:: ግን ገና የ33 ዓመት ወጣት
እና እንደ ፈረስ ጠንካራ ነበር።”

“ቲና አሁንም ሰዎች እየተገደሉ ነው” አላት እና ዊሊያምስ በመቀጠልም
“እኔም እዚህ የተገኘሁት በዚህ ምክንያት ነው” አላት፡፡

በመቀጠልም ስለ ሊዛ ፍላንገንን እና ትሬይ ሬይሞንድ ግድያ ሟቾቹ
ከኒኪ ሮበርትስ እና ከባሏ ዶውግ ጋር ስላላቸው ግንኙነት ሮበርትስ ስላለው
ከአደንዛዥ ዕፅ ጋር ስለሚገናኝ የበጎ አድራጎት ሥራዎቹ እና በሎስ አንጀለስ
ላይ የበላይነቱን ለመያዝ ሩስያኖቹ እና ሜክሲካኖቹ ስለሚያደርጉት ግብግብ
ጭምር ነገራት፡፡

“ዶውግ ሮበርትስ ባለፈው ዓመት ነው በአደጋ ህይወቱን ያጣው:: ከጎኑ
ደግሞ ለከንቲባ ፋንቴስን መኪና ከሚሰጡት ሩስያውያን ጋር ግንኙነት ያላት
ሴት ነበረች። እሷም በአደጋው ሞታለች” አላት፡፡

ቲናም እጇን አንስታ “ሙስና ነው ያልከው? አድሬኒ ናት ይህንን የነገረችህ? በእግዚአብሔር ሥም ይህቺ ልጅ በቅርቡ ትገደላለች እመነኝ:: ደግሞ የሚገርመው ነገር እኮ እሷ ስለጉዳዩ ምንም የምታውቀው ነገር ያለመኖሩ ነው::” አለችው፡፡

“ልክ ብለሻል እኔም እንደ አንቺ ነው የማስበው” አላት ዊሊያምስ፡፡

“በመጀመሪያ ደረጃ እኔ ፋንቴስ በግሉ ጉቦ ይቀበላል አይደለም ያልኩት።
ግን ማዘጋጃ ቤቱ ለእሱ ባወጣለት የባንክ አካውንት በኩል የተለያየ አይነት
ገንዘቦች ይገቡለታል ነው ያልኩት። የማወራህ ስለ ትልቅ ክፍያዎች ሲሆን
ክፍያውን ደግሞ የሚፈፅሙት ሩሲያዎኖቹ ናቸው”

ዊሊያምስም ማስታወሻ ደብተር ላይ እየፃፈ “ምን ያህል? እና ደግሞ
የትኞቹ ሩሲያኖች?”

“መጠኖቹ በየጊዜው ይለያያሉ።” አለች እና ቲና በመቀጠልም

“አምስት መቶ ሺ ዶላር መቶ አምሳ ሺ ዶላር እና አንድ ጊዜ ደግሞ አንድ ሚሊዩን ዶላር፡፡ ብቻ በየአራት እና በየስድስት ሳምንቱ የተለያዩ ቼኮች
ይመጣሉ፡፡ ለማንኛውም ባጠቃላይ ወደ ሦስት ሚሊዩን ዶላር ይሆናል።”

“እሺ ክፍያውን የሚፈፅሙትን የሩሲያኖችን ሥም ታውቂዋለሽ?”
አላት፡፡

“አላውቅም” ብላ ወደ ወለሉ
ተመለከተች:: ዊሊያምስ ቲና በጣም
እንደፈራች ተመልክቶም

“እነርሱን የምትገልጪበት አካላዊ ሁኔታቸው? በአካልስ አግኝተሻቸው
ታውቂያለሽ?” ብሎ ጠየቃት። ቲናም ራሷን በአሉታ በሀይል ካወዛወዘች
በኋላ ከንፈሯን ነክሳ “ይቅርታ ይህንን ልነግርህ አልችልም” አለችው፡፡
የስልክ ጥሪዎችን ቢያንስ ተቀብለሽ ታውቂያለሽ? ወንዶች ናቸው ሴቶች?
ሁለት ናቸው ወይንስ ሃያ?”

“አይገባህም እኮ...”

ሌንካ ጎርደቪስኪ የምትባል ሴት ታውቂያለሽ?” ብሎ አይፎን ስልኩን
አወጣና የጎርዴቪስኪን ፎቶ አሳያት። የቲና አይን ላይ ሌንካን እንዳስታወሰች
የሚያሳብቅ ዕይታን ዊሊያምስ ተመለከተ።

“ዴ.ሪክ ስለዚህ ነገር መናገር አልችልም። እስከ አሁንም በጣም ብዙ ነገር
ነው የተናገርኩት”

“ቢያንስ የአንድ ካምፓኒ ሥምን ንገሪኝ፤ ያላወቅኩትን እንቆቅልሽ የምፈታበትን አንድ ነገርን እንኳን ንገሪኝ” ሲላት ጊዜ አናቷን በሀይል ወዝውዛ ይገድሉኛል!” አለችው፡፡

ዊሊያምም ለጥቂት ጊዜ ያህል አፍጥጦ ሲያያት ቆየና በቀስታ “ምናልባት ይገድሉሽ ይሆናል። ምናልባት ሁለታችንንም ይገድሉን ይሆናል፤ ግን አንቺ የያዝሺው ሚስጥር እንደወጣ በማሰብ ሌሎች ሰዎች እየተገደሉ ቢሆንስ? ይህንን ግድያቸውን የሚያስቆመው ደግሞ አንቺ
የያዝሺውን ሚስጥር ይፋ በማውጣት ነው። ይህንን ነገር አምነሽ አይደል
እንዴ ለሮቢን ሳንፎርድ ስልክ የደወልሺው?”

“አዎን” አለች እና ቲና ታፋዋ ላይ ያስቀመጠችው እጇ ይንቀጠቀጥባት
ጀመር፡፡ “በጣም እንደፈራሽ አውቃለሁ። እኔም እኮ በጣም ፈርቻለሁ፤ ቲና
ግን ይሄንን እኛ ካልተናገርን ማን ይናገራል እሺ?”

ዴሪክ ዊሊያምስ ከጎኑ በተቀመጠችው ሴትዮ ውስጥ የሚካሄደውን የሀሳቦች ፍልሚያን አሰበ። ቲና ድሬይተን በጣም ደፋር ሴት ነች። ይህንን ደግሞ አንድ ጊዜ ለማረጋገጥ ችሏል። ግን ሁሉም ሰው የድፍረት ገደብ አለው።
“እሺ” አለች እና በመጨረሻም “እነግርሃለሁ። ግን ከዚህ በኋላ እኔን ዳግመኛ በፍፁም ለማግኘት እንዳትሞክር፡፡ በፍፁም! ለማንኛውም ምክንያት ቢሆን።

ዊሊያምም ወንበሩ ላይ ተመልሶ ቁጭ አለ እና


“ይሄው ቃሌን እሰጥሻለሁ” ብሏት እስክሪብቶውን አወጣ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ኒኪ እና ግሬቸን ገና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እያሉ ይሄዱበት ወደ
ነበረው የኮሪያውያን ፍልውሃ ውስጥ ራቁታቸውን ሆነው ሰውነታቸውን
እያደሱ ነው። ግሬቸን የወረዱ ጡቶቿን ከኒኪ ብርትኳን ከሚያካክሉ ጡቶች
ጋር፣ ሽንትርትር ያለውንና ዘልዘል ያለ ሆዷን ደግሞ ልጥፍ ካለው የኒኪ
ጡቶች ጋር አነፃፀረች፡፡ ጡቶቿ ሦስት ልጆችን ያጠባ እና ሆዷም ሦስት
ልጆችን የተሸከመ በመሆኑ የተነሳ እንደዚህ እንደሆነ አሰበች እና ተፅናናች::

ኒኪ ውሃው ውስጥ ሙሉ በሙሉ ሰምጣ ከወጣች በኋላ የሴት ወሬያቸውን ጀመረች “ባለፈው የነበረው የእራት ግብዣ ላይ ሀዶን አስገድዶ ሳመኝ፤ ከበፊት ጀምሮም እወድሻለሁ አለኝ” አለች ኒኪ ላግሬቸን፡፡

ግሬቸንም “እኮ የኛ ሀዶን ነው?” ብላ ተገርማ ጠየቀቻት፡፡

“አዎን፣ ግን ጥሩ ስሜት አልተሰማኝም። ምክንያቱም እሱ እኮ ለዶውግ
ልክ እንደ ወንድሙ ነበር፡፡

“አአ ልክ እንደ ኦሪት ዘመን ነዋ? ማለትም አንዲት ሴት ቧሏ ከሞተ ወንድምዬው እንደሚጠቀልላት አይነት ነገር መሆኑ ነዋ” ብላ ግሬቸን አሾፈችባት፡፡

ኒኪም በግሬቸን ሹፈት ትንሽ ተከፍታ ዝም አለች። ግሬቸን ይሄ የኒኪ ጥቁር ደመና እስኪያልፍ ድረስ ዝም ብላት ውሃው ውስጥ ብቅ ጥልቅ ስትል ቆየች፡፡

ከጥቂት ጊዜ በኋላም ኒኪ “ይሄውልሽ ግሬች እኔ ችግር ሳይኖርብኝ
አይቀርም፡፡ ምንም አይነት የወሲብ ፍላጎት እንኳን የለኝም”
👍4
አለቻት፡፡

“የኔ ቆንጆ ይሄ እኮ ችግር አይደለም፤ ሀዘን ላይ ስለሆንሽ ነው”

“እንዴ ዓመት አለፈኝ እኮ” ብላ ኒኪ መለሰችላት፡፡

“በዙሪያሽ የተከሰቱት ግድያዎቹስ ቀልድ ናቸው እንዴ? እንዲያውም አንቺ ሆነሽ ነው ሌላ ሰው ቢሆን ያብድ ነበር።”

“ይልቅ የሆነ ስውን እያሰብኩኝ ነው” ብላ ኒኪ ፊቷ በእፍረት እየቀላ ለግሬቸን ነገረቻት፡፡
ግሬቸንም ወሬውን ለመስማት ጓግታ “ደግሞ ማነው?”

“ኧረ ያን ያህል እኮ አይደለም” አለቻት ኒኪ፡፡

“ማን ነው እኮ ነው ያልኩሽ?” ብላ ግሬቸን ሳቀችባት፡፡

ኒኪም ፍልቅልቅ እያለች “ሉው ጉድማን ይባላል፡፡ ከመርማሪዎቹ ውስጥ
እንዴ እኔን በግድያው ወንጀል ይጠረጥረኛል ያልሺው ሰው ነው?”
“አይደለም እሱማ ባልደረባው ነው። ጉድማን መልከ መልካም እና ለእኔ
አሳቢ ነገር ነው። በዚያ ላይ ደግሞ ጨዋ እና ቀና ሰው ይመስላል፡፡

እየተባባሉ ትንሽ ሲያወሩ ቆዩ፡፡ ኒኪ ይበልጥ እያፈረች እና ጓደኛዋ
አይሆንም እንድትላት እየፈለገች “ይልቅ ለአንዲት ታካሚዬ የተለየ ስሜት
ሳይስማኝ አይቀርም። ባለፈው የቀጠርኩት የግል መርማሪዬ እንደነገረኝ
ከሆነ ይህቺ ሴትዮ አንድ የአደንዛዥ ዕፅ አምራች ከበርቴ ሚስት ናት።ወጣት ናት፡፡ ባሏን ትታ ነው እዚህ ሎስ አንጀለስ ውስጥ የምትኖረው::”

“ከዚህ በፊት ከሴት ጋር አድርገሽ ታውቂያለሽ እንዴ?”

“በጭራሽ” አለች ኒኪ፡፡

“ኮሌጅም እያለሽ?”

“ሂጂ አብረን አልነበርን እንዴ? ባደርግማ ታውቂ ነበር” ብላ ስትመልስላት ግሬቸንም “እውነትሽን ነው ቢኖርማ ኖሮ አውቅ ነበር” አለቻት፡፡

“ይመስለኛል የመካከለኛ ዕድሜ ውዝግብ ውስጥ ሳልሆን አልቀርም...”
አለች እና ኒኪ ወደ ሀዘን ደመናዋ ውስጥ ተደበቀች፡፡ ይህ ስሜቷ ባሏ ከሞተ በኋላ ለተደጋጋሚ ጊዜ የሚሰማት መሆኑን የምታውቀው ግሬቸንም እንደ ሁልጊዜውም ሁሉ ኒኪ ከዚህ ስሜቷ እስክትወጣ ድረስ ዝም ብላ ጠበቀቻት።

ኒኪ ወደ ጥሩ ስሜቷ ስትመለስም ግሬቸን ስለ ልጆቿ የተለያዩወሬዎችን እያወራችላት ውሃው ውስጥ ቆይተው ሲበቃቸው ወደ መታሻው ክፍል ገቡ። መታሻው ክፍል ውስጥም ሰውነታቸው ፍም እስኪመስል ድረስ
በደንብ ከታሹ እና ሰውነታቸው ከተፍታታ በኋላም ልብሳቸውን ለብሰው ከኮሪያውያን የፍል ውሃ ቦታ ወጡ እና ወደ ሱሺ ባራቸው አመሩ፡፡....

ይቀጥላል
👍3
#የወድያነሽ


#ክፍል_አምስት


#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል


....የአባቴ ተራ ድንጋጤና የእናቴ ያልታሰበ ተራ ድንፋታ ልቤን በደስታ አክናፍ አበረራት፡፡ የአባቴ ድብቅ ፍላጎት ሳያስበው በመጋለጡ የሁለቱ ፋይዳ ቢስ ጠብና ስሜት ለስሜት መሳለል በጣም ቢያስደስተኝ ምናልባት እናቴ በዚሁ በሰማችው ብቻ ቅናቷ እያደር ይጎለምስና የወዲያነሽን ታባርራት ይሆን? በማለት መጪውን ጊዜ በሥጋት ዐይን ተመለከትኩት የጨዋነቱ ክብር» የተገፈፈበት የመሰለው አባቴ ያ አይበገሬ መሳይ ወኔው ላመል ታህል በርግጎ ከቆየ በኋላ ለመከላከል ያህል «አማረባት አልኩ እንጂ ምን ሳደርግ አየሽኝ? እኔ ያየህ ይራድ ከማንም ብራሪና ውዳቂ ጋር የምልከሰከስ ነኝ እንዴ? ከጠረጠርሽኝ፣ ዛሬውኑ! አሁኑኑ መንጥቂያት!» ብሎ በንዴት ወደ መኝታ ቤት ገባ፡፡

የእናቴ ፊት በቁጣ ተከስክሶ ዐይኖቿ በሽሙጥ ሸኙት። ነገሩ ተባብሶና
እንደገና ሌላ ነገር ጭሮ ውጤቱ መጥፎ አይሁን እንጂ እሳትና ጭድ ያድርጋችሁ
ማለቴ አልቀረም፡፡

ከአባቴ ይበልጥ ያናደደኝና ውስጥ ውስጡን ያበሳጨኝ ግን የቤታችን
ዘበኛ ነበር። በእርሱ የተነሣ ልቤ በቅናት እሳት ተለብልባ ተሠቃይታለች።

በመልኩ፣ በሰውነት አገነባብና ለግላጋነት ከምኑም አልደርስ። ፈገግታውና የባቄላ አበባ የመሳሰሉ ጥርሶቹ ይማርካሉ። በሥራ ምክንያት በምድረ ግቢው ውስጥ ከወዲያ ወዲህ ሲል ከየወዲያነሽ ጋር የተገናኙ እንደሆነ ተሣሥቀውና ተጠቃቅሰው ይተላለፋሉ፡፡ ከነዚያ ልበሳቸው ብዬ ከሰጠሁት ሸሚዞችና ሱሪዎች መካከል የለበሰ ለትማ ማለፊያ ሙሽራ ስለሚመስል ለባብሶ ባጠገቧ ሲያልፍ ዐይኖቼ በቅናት ደም ይለብሳሉ። አውልቅ ብዩ የምነጥቅበትና ሰበቡ የማይደረስበት ስውር ደባ በማጣቴ ሐሳቤ እንደ ጨው ሟምቶ ቀረ።

ለሥራው ደፋ ቀና ሲል ሰርቄ ሽንት ቤት ውስጥ ለመክተት ያሰብኩበት ጊዜም ነበር፡፡ አንድ ቀን ማታ እርሱና የወዲያነሽ ተከታትለው ወደ ማድቤት
ሲገቡ በማየቴ ጨለማ ለብሼ ከአንድ ትይዩ ቦታ ላይ ከሩቅ አደፈጥኩ፡፡ ከአንድ
ጐድጓዳ ሳህን ውስጥ ፍትፍት ቢጤ ሳይሆን አይቀርም ቶሉ ቶሉ እያወጡ ግራና ቀኝ ቆመው መብላት ጀመሩ። አንድ ሁለት ጊዜ ያህል ለራሷ ትጎርስና ለእርሱም ያንኑ ያህል ታጐርሰዋለች። የአፉን ውስጥ አላምጦ ሳይውጥ ሌላውን ከከንፈሩ ጫፍ ትደቅንለታለች፡፡ ፍትፍት መሆኑ በግምት የሚያስታውቀው ከጉርሻዋ በኋላ ጣቶቿን በማራገፏ ነበር። ከቅናትና ከጥላቻ ብዛት የተነሣ ቁርጠት የቀሠፈኝ ይመስል ሰውነቴ ብው ብሉ- አንጀቴ በንዴት ተቋጨ።

«ና ውጣ ብዬ እርሱን ከእርሷ ነጥዩ የማስወጣበት ምክንያት እንደ ሰማይ
ኮከብ ራቀኝ፡፡ ነገር ግን ወዲያው አንድ ቀላል ነገር ትዝ አለኝ። ቀስ ብዬ
እያሰላሁ እንድ አራት ያህል ደህና ደህና ድንጋይ ከለቀምኩ በኋላ ትልቁን
የአጥር በር በድንጋይ ጠመድኩት።

አራት ጊዜ ያህል እንደ መታሁ ጅብ እንዳየች ቡችላ ሳህኑን ለቆላት ተፈተለከ፡፡ እሷ የበሩን መቃን ተደግፋ ቆመች፡፡ የወዲያነሽንም በመጠኑ ለማስደንገጥ ያህል አንዲት ትንሽ ድንጋይ ወደ ማድ ቤቱ በር እነጣጥሬ ወረወርኩ፡፡ በቀጭን የድንጋጤ ድምፅ «ውይ» ብላ ወደ ውስጥ ሮጠች። የሁለቱም ትኩስ ድንጋጤ ሳይበርድ ልክ ከቤት እንደ ወጣ ሰው ተመስዩ ከተደበቅሁበት ቦታ መሰስ አልኩና «ማን ነው? የማን ነው ባለጌ በጨለማ በር የሚደበድብ?» ብዬ ጮህኩ፡፡ ማንም አልመለሰልኝም፡፡

ዘበኛው የወረወረውን ሰው ለማወቅ በሩን ከፍቶ ወጣ፡፡ ባልተረጋገጠ የቅናት መነሾ የፈጸምኩት የተንኮል ድርጊት ራሴን እያሳፈረኝ እፈን አፍኜ ሣቅሁ፡፡ ነገር ግን ወደ ውጪ በመሄድ ፈንታ ወደ ቤት ገባሁ፡፡ ሆኖም መቀመጥም መቆምም የሚነሳ አንዳች ውስጣዊ ግፊት መላ አካላቴን ናጠው፡፡ አልቻልኩትም::

ሩብ ሰዓት በማይሞላ ጊዜ ውስጥ የወዲያነሽ ዕቃ ቤት ውስጥ
ስትንጐዳጉድ እገኘኋት። ጣቴን በቁጣ እየነቀነቅሁ «ከዚያ ከመድረሻ ቢስ ሴት
አውል ዘበኛ ጋር ያደረግሽውንና የምትሠሪውን ያላወቅሁ እንዳይመስልሽ!
የመጣው ይምጣ እንጂ የማደርገውን ዐውቃለሁ፡፡ እኔ ጌታነህ ትርክርክሽን ነው
የማወጣው» ብዬ አፍጥጨባት ተመለስኩ፡፡ ክፉኛ ክው ብላ ነበር።
በስውርና በግልጽ መቆጣጠሬን ቀጠልኩ፡፡ የወዲያነሽ ከእኔ ጋር ምንም
ዐይነት ፍቅራዊ ስሜትና ዝንባሌ እልነበራትም፡፡ ስለሆነም ስለ ግንኙነታችን
የምታደርገው አንዳችም ጥረት አልነበረም፡፡ ይህም ሊሆን የቻለው «ሊያታልለኝና የምመልስለትን ለማወቅ ፈልጎ ነው» ብላ እንደሆነ እያደር ተገለጸልኝ፡፡

«ከዘበኛው ጋር ስትዳሪና ስትላፊ አይቼሻለሁ» ብዩ ከገሠጽኳትና
ከተንደራራሁባት ወዲህ ግን ወይ በፍርሃት አለበለዚያም በውስጧ ተሰዉሮ በነበረ ለጋ ውዴታ ምክንያት እርሱን ችላ ብላ ወደ እኔ መለስ አለች፡፡ ሆኖም
በቀድሞው አንገተ ሰባራነቷ ላይ በፍርሃትና በበታችነት ስሜት በመጠመዷ
የዝቅተኝነት ጭንቀት አጠቃት።

አንድ ቀን ማታ ከእኔና ከእርሷ በስተቀር መላው ቤተስብ ከላይ እታች በተኛበት ወቅት ኮቴዬን ሳላሰማ ከመኝታ ቤቴ አስልቼ ወጣሁ፡፡

ዕቃ ቤት ውስጥ ወዳለው ወደ የወዲያነሽ መኝታ ክፍል ለመሄድ እንግዳ መቀበያ ክፍል ውስጥ ስደርስ ከበሩ አጠገብ ቆማ አየኋት። የተከፈተውን የዕቃ ቤት መዝጊያ ተደግፋ ቆማለች። አንዲት አራት ማዕዘን መስተዋት በግራ እጅ ይዛ በመስታወቱ ውስጥ ከምታየው ከሌላዋ ነፍስ አልባ «እርሷ» ጋር ፈገግ እያለች ትሥቃለች። ቀና ብላ በድንጋጤ ካየችኝ በኋላ በምን ይለኝ ኀፍረት በእጅዋ የያዘቻትን መስታወት ከቀኝ እጅ ብብቷ ውስጥ አጣብቃ ይዛ አቀርቅራ ቆመች። እግሬ ላይ መጫሚያ ባለመኖሩ በለስላሳው እግሬ ያደረግሁት እርምጃ በሥጋጃ ላይ የምትራመድ የድመት አካሔድ ሆኖ ነበር፡፡

እጠገቧ ደርሼ ቆም ስል ወደ ጎን ሽርተት አለች። ገፋፍቶ ያስወጣኝ ድፍረት እንደ ቅቤ ቀለጠ። ሰውነቴ በኃፍረት ተተብትቦ ግድግዳውን ተደግፌ ቆምኩ፡፡ አወጣጡ ግን ግድግዳ ተደግፌ ለመቀም አልነበረም፡፡

ትሰድበኝና አጉል ታዋርደኝ ይሆን» እያልኩ በፍራቻ ስሜት ውስጥ
ከቆየሁ በኋላ «እስካሁን ምን ታደርጊያለሽ የወዲያነሽ?» ብዬ ለማሽኮርመም ያህል ባቀጠንኳት ድምፅ ጠየቅኋት። እንዳቀረቀረች አሻግራ ወለል ወለሉን እየተመለከተች «ማድ ቤት ወርጀ ገላዩን ስታጠብ ቆየሁና ይኸ ጸጉሬ
እንዳያስጠላ ከመተኛቴ በፊት ልጎንጉነው ብዩ ነው» ብላ ዝምታዋን ተያያዘችው፡፡

ምናልባት ያ መዘዘኛ ዘበኛ ገብቶ አጫውቷት ይሆን? በማለት መላ
ሰውነቴ በቅናት ግው ብሉ ጋየ፡፡ «መታጠቡንስ ጥሩ አደረግሽ፡ ለመሆኑ ግን እያሸሽ ታጠብሽ?» ብዬ ጠየቅኋት።
“አስካለ፣ እስካለ ናት ፍትግ አድርጋ ያጠበችኝ» ብላ ንግግሯን ሳትጨርስ በቅናት የተሥረቀረቀ ልቤን ለማፅናናት «እኔስ ያ ዘበኛ ነው ብዬ አልኳት፡፡ ፊቷ ጠወለገ፡፡ ከወደ ውስጥ የሚወጣውን ትካዜዋን ይገልፅ ይመስል የቀኝ እግሯን ሰበር አድርጋ «ውይ! ምነው ምን አልኩዎት፡ ከዚያች እርስዎ ከተቆጡኝ ቀን ወዲህ ቀና ብዬም አይቼው አላውቅ:: እኔስ ይቺው የድሃ እንጀራዬ ትበልጥብኛለች» ብላ ከፊቴ ላይ ሁኔታዬን ለመረዳት ሰረቅ አድርጋ አየችኝ። ነገሩን ለማቃለልና የእርሷም ያልተዘጋጀ እእምሮ ምን መልስ እንደሚሰጥ ለማወቅ ስል የቀኝ እጅ ጣቶቿን ያዝ አደረግሁና እረ ለመሆኑ እኔ እንደምወድሽ ታውቂያለሽ ወይ?» ብዩ በሙሉ ድፍረት ጠየቅኋት። ሆኖም ዝምታዋን ጥሶ የሚወጣ የመልስ ቃል ሳላገኝ ቀረሁ። አገጯን ይዤ ወደ ላይ
ቀና አደረግኋት። ያቺን ለስላሳ የምታምር ድቡልቡል እገጯን ስነካ ሰውነቴ
ውስጥ ተናዳፊ ንዝረት ለቀቀብኝ። እንደ ዱር ሀረግ አንገቷ ላይ ተጠምጥሜ
ብስማት እፎይታ እንደማገኝ ታወቀኝ፡
👍5
፡ ሆኖም ያንኑ ያሀል ኃፍረትና ወኔ ቢስነት
በላዩ ላይ ስለ ተቸለስ ሟሽሼ ቀረሁ፡፡

«ንገሪኝ እንጂ ለምን ዝም ትያለሽ? ሰው ሁሉ እስኪተኛ ድረስ ጠብቄ የመጣሁት እኮ እንድትነግሪኝና ቁርጤን እንዳውቅ ብዬ ነው» አልኩና የያዝኩትን እጅዋን ትከሻዬ ላይ ሰቀልኩት። ብብቷ ሥር የነበረችው መስተዋት ወደቀች፡፡
አልተሰበረችም፡፡ እጇን ትከሻዬ ላይ የሰቀልኩት በእሺታና በፍቃዷ ባለመሆኑ
የጓያ ፍንካች የምታህል ደስታ አልተሰማኝም፡፡ አሁንም ቢሆን ከዝምታዋ ጥልቀት ውስጥ መልስ ማግኘት ባለመቻሌ ልቤ በንዴት ተጥመለመለች። ሳልወድ በግድ ለቅቄያት ወደ መኝታ ቤቴ ተመለስኩ፡፡ ሥጋዊ አካሌ ዟ ብሉ ሲንጋለል አእምሮዬ ግን በሐሳብ ዋዠቀ፡፡ ከራሴ ጋር ክርክር ገጠምኩ፡፡

ሐሳቧንና አስተያየቷን ሳላጠናና ሳላውቅ «ወደድኩሽ ብዩ ለምን ዘላበድኩ? «ምናልባት ይህን ነገር እንደ ክብር ቆጥራ ያላልኳትንና ያልጠየቅኋትን ሁሉ ጨምራ ጨማምራ ታወራ ይሆን?» በማለት ከአንድ ሰዓት በላይ እየተሠቃየሁ ተገላበጥኩ። ተጸጸትኩ። ጸጸቴ ግን እንደ አለብላቢት ቅጠል አእምሮዬን ለበለበው እንጂ ሌላ ፍቺ አልሰጠኝም፡፡ ሐሳቤን አንድ ፈር ሳላሲዝ አንቀላፋሁ። ጊዜው ጐረፈ።

ዘወትር እሑድ እሑድ ከቤተ ክርስቲያን መልስ ረፋዱ ላይ የሚፈላው ቡና የተለየ ክብርና የአከታተም ዝግታ አለው፡፡ በአጋጣሚ እሑድ ላይ ተደርቦ የሚውል ዕውቅ ተራዳዒ ቅዱስ መልኣክ ወይም ባለገድል ሰማዕት ከዋለ እሑድ
ተጣማሪ የክት ስም ይሰጠዋል፡፡

ዕለተ ሰንበትና ሥላሴዎች ናቸው:: ዕለተ ሰንበትና ሊቀ መላኩ ነው፣ ዕለተ ሰንበትና እመ ብርሃን ወላዲተ አምላክ ናት ይባልና ሦስት አራት እነባበሮ በቅቤ ጫፍ እስኪል ርሶ ይቆረሳል ጾም ካልሆነ። ውለታ የዋለና ስለት ያደረሰ ታቦት ለሆነማ አንድ ሁለት ጋን ጠላና ሾላ የመሰለ ድፎ ዳቦ አያጣም፡፡ ምን ጠፍቶ

ያንድ ቀን ለታው እሑድ ባለ አጋጣሚ ተረኛ መድኃኔዓለም ስለ ነበር እናትና አባቴ ስደተኛው መድኃኔ ዓለም አስቀድሰው እንደተመለሱ እንግዳ
መቀበያ ክፍል ውስጥ ቡና ተፈልቶና አነባበሮ ተቆርሶ የቤተሰብ ወሬ ደራ፡፡ ስለ
አገር ቤትና ስለ ከተማ፣ ስለ ዘመድና ባዳ ሙገሳና ወቀሳ አንዱ ካንዱ እየተቀበለ
አወራ።

እናቴ በግልጽ ስለምታውቃትና ስለ ተካሠችባት የአባቴ የቀድሞ ወጻጅ
ስለተጠረጠረባቸው ሴቶች እንኳ ሳይቀር እንደ ቀልድ እየተነሣ ተሣቀ፡፡
የወዲያነሽ ድንገት ብድግ ብላንደ ዕቃ ቤት ሄደች። ያረጀ ያፈጀ ወሬ ስለነበር
አልታፈረበትም በመኻሉ በእናቴ አእምሮ ውስጥ የየወዲያነሽ ሐሳብ ድንገት
ድንቅር ብሎ ኖሮ እናቴ ተዘብንና ሳቀችና ያንተ ነገር ደግሞ ምን ማለቂያ
አለው? መቼም ልብ እይሞት! ውሽትና ስንቅ እያደር ይቀላል ከሚሉ ወንድና
ስንቅ እያደር ይቀላል ቢሉ ኖሮ ጥሩ ነበር፡፡» አለችው ሕሊና በማይጎዳ ሽሙጥ
«አፍ ተጅ ባይሆንብህ ኖሮ እንዳንተ አስተያየትማ የትናየት በተዳረስን ነበር፡፡
ብላ ስለማን መናገር ላይ እንደፈለገች እንዲያውቅ ላፍታ ያህል ትኩር ብላ
አየችውና “ደግነቱ የሷ ቀና ተብላ
ሰው ያለ ማየት በጀ እንጂ ብላ በወሬ መኻል የቀዘቀዘች ቡናዋን ጨልጣ ንግግሯን እንደ መቀጠል ስትል
«አንቺም እኮ እንደዚያ ዕለቱ አድርገሽ አዋርደሽኝ አታውቂ! በሌላ ነገር
ቢሆን እንዴት ደስ ባለኝ፡ ሚስት ገመና ከታች ናት ይባል ነበር፡፡ እኔ ላይ
በስተርጅና ታዘብኩሽ! አንዲት ቃል ሳት ብላኝ ብታመልጠኝ እንዴት ከገረድ
ጋር ታውይኝ?» አለና አባቴ ያለፈውን ንዴትና ቂሙን ከወቀሳ ጋር አደባልቆ
ተናገረና መጽሐፉን ለመመልከት አቀረቀረ።

«ያልጠረጠረ ተመነጠረ» አለች እናቴ በአነጋገሯ ኩራትና ግድየለሽነቷን
እያሳወቀች፡፡ «ታዲያ የማንም ብራሪና መድረሻ ቢስ በስተርጅና ትዳሬን
ትበትነው ብለህ ነው?» ብላ ወደ እኔና ወደ የውብነሽ ተመለከተች። በእንግዳ
መቀበያው ክፍል ውስጥ ከአራታችን በቀር ሌላ ሰው ባለመኖሩ አባቴ በጉዳዩ ላይ ተዝናንቶ ለመናገርና ንጽሕናውን ለመናዘዝ ይሉኝታ እልተጫነውም፡፡

ከሚያነበው መጽሐፍ ላይ ቀና ብሎ ከሠላሳ ስድስት ዓመት በኋላማ
ኸገረድ ተገናኘ፣ ተጠረጠረ ብባል የሞት ሞት እይደለም ወይ? እንዴት ብዬ
አደባባይ ልወጣ? በመጠርጠሬ እንኳ ቆሽቴ ተልጧል። ትልልቆቹስ ሥፍራ
ሥፍራቸውን ይዘዋል፡ እነኚህ ምን ይሉን?» ብሉ» ራሱን ነቀነቀና እንደገና ወደ መጽሐፉ መለስ አለ።

«እስኪ እንዲያው ተካበች ሙች፣ ፍቅራችንን በለኝ፡ ልቦናህም አልከጀላት?» ብላ ጠየቀችው:: የዝቋላው ና» ብሎ በመሐላ ነገሩን ከሥር ከመሠረቱ መንግሎ በመጣል ከጥርጣሬ ቅጥር ውጪ አሽቀነጠረው፡፡

የወዲያነሽ ስለ እርሷ ምን እንደተባለና እንደተወራ ባለማወቋ ሥራዋና ሁኔታዋ ሁሉ አልተለወጠም። ይልቁንም ለእናቴ ያላት አክብሮትና ታዛዥነት እያደር በመጨመሩ ሁሉንም ነገር የቸልታ ጉሮሮ ዋጠው:: የእናቴም ጥርጣሬ
በአባቴ መሐላ እንደ ጢስ በንኖ ጠፋ፡፡ አባቴም ከዚያ ወዲህ ስለ የወዲያነሽ
አኳኋንና አሠራር ትንፍሽም አሌለ።

እኔና የወዲያነሽ ከቀድሞው በበለጠ ሁኔታ ጠባይ ለጠባይ በመተዋወቃችንና በመግባባታችን ምን ጊዜም አንድ እፍኝ ሙሉ ፈገግታ ፈገግ ባልኩላት ቁጥር አጸፋውን በእንቅብ መቀበል ቋሚ ልማዳ ሆነ፡፡ የወዳያነሽ አእምሮ ውስጥ ብዙ አስጨናቂ የሐሳብ ውጣ ውረድ እንደሚተራመስ የሚታወቀው ከእያንዳንዱ ፈገግታ በኋላ ፊቷ ስለሚጠወልግ ነበር።

💫ይቀጥላል💫
👍5
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_አርባ_ስድስት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

...ከኮሪያውያን የፍል ውሃ ቦታ ወጡ እና ወደ ሱሺ ባራቸው አመሩ፡፡
ሱሺ ባር ውስጥም ተቀምጠው እየበሉ እያሉ ግሬቸን “ይህንን ቀጠርኩት
ያልሺውን የግል መርማሪሽን ከየት ነው ያገኘሽው?” ብላ ኒኪን ጠየቀቻት፡፡

ኒኪም “ከጎግል ላይ ነው:: ስለ እሱም በደንብ አድርጌ ካነበብኩኝ በኋላ
ነው የቀጠርኩት፡፡ ይልቅ ከ 10 ዓመት በፊት ለማን ተቀጥሮ ይሰራ እንደነበር እስቲ ገምቺ?”

ግሬቸንም በኒኪ ጥያቄ ከት ብላ ከሳቀች በኋላ “እኔ ይሄንን እንዴት ላውቅ እችላለሁ፡፡ በይ ንገሪኝ እስቲ”
“ለክላንሲ ቤተሰቦች ነበር። ባለፈው ምሳ ስንበላ እንዲያውም አንቺ ነሽ የነገርሺኝ፡፡ ሜክሲኮ ውስጥ ጠፋች ምናምን ብለሽ፡፡ ትዝ አለሽ?”

“አዎ ቻርሎቴ ክላንሲ። አባቷ የእሳት አደጋ ሠራተኛ ነው::”

“ልክ ነሽ ተከር ክላንሲ ይባላል፡፡ ባይገርምሽ እሷ የእኔ ታካሚ ከሆነች
አንዲት ሴት ባል ጓደኛ ጋር ግንኙነት ነበራት። የክላንሲ ወዳጅ ባንከር ሲሆን
የሚሰራው ደግሞ ሮድሪጌዝ ከሚባል የአደንዛዥ ዕፅ አምራች ባለቤት ጋር
ነው:: የአደንዛዥ ዕፁንም እዚህ ሎስ አንጀለስ ውስጥ እየሸጠ ነው ብሎ ነው
ዴሪክ ዊሊያምስ የሚባለው መርማሪዬ የነገረኝ” አለቻት ኒኪ፡፡

ግሬቸንም ጓደኛዋ በዚህ መልኩ ነግሮችን እያገናኘች ማሰቧን እና መርማሪዋ የነገራትን ሁሉ አምና በመቀበሏ እየተገረመች እያየቻት

“እሺ ከዚያስ የክላንሲን ቤተሰብ ጉዳይ ይዞ የነበረው መርማሪሽ በመጨረሻ ላይ ምን ሆነ?” ብላ ኒኪን ጠየቀቻት፡፡

“አባረሩት”
“ለምን?”
“ምክንያቱም ቻርሎቴ ከባለትዳር ጋር ግንኙነት ነበራት ብሎ ስለነገራቸው ነው፡፡ በነገራችን ላይ ቻርሎቴ ጨዋ አልነበረችም። እሷ ሜክሲኮ ላይ የሰው ትዳር ለማፍረስ ስትንቀዥቀዥ የነበረች ሴት በመሆኗ የእጇን ነው ያገኘችው። ስለዚህ አላዝንላትም” አለች ኒኪ ትንሽ ምሬት ባዘለ ድምፅ፡፡

ግሬችንም ቀና ብላ በቅሬታ እያየቻት ኒኪ ከመቼ ጀምሮ ነው ደግሞ በሰዎች ሞት ደስተኛ መሆን የጀመርሺው? መቼስ አንዲት ሴት ከባለትዳር ጋር የፍቅር ግንኙነት ስላደረገች ትሙት ብለሽ አትፈርጂም?” ብላ ጠየቀቻት፡፡
“ለምን ብዬ ነው የማልፈርደው?” ብላ በቁጣ በሚንቀለቀል አይኗ አየቻት
እንደቀልድ ስታይ አዳም ሲያቀብጣት የነበረች አንዲት ሸርሙጣ ሴት እና” የሆነ ማታ ላይ የአዳምን አይ ፓድ ስትከፍቺ እና ፎቶዎችን የራቁት ፎቶን ብታይስ ምን ይሰማሻል?”

“በእርግጥ ነገሩ ያሳቅቃል፡፡ ግንንንን...”
እሺ ልጅቷ እርጉዝ ብትሆንስ?” ብላ ኒኪ ልክ ሰይጣን እንደያዘው ሰው
ጮክ ብላ መለፍለፍ ስትጀምር ቤቱ ውስጥ ያሉ ሰዎች ዞር ዞር እያሉ ወደ
እነርሱ መመልከት ጀመሩ። “እሺ አንቺ ለባለፉት አምስት ዓመታት ያህል
ውጤት አልባ እና በጣም የሚያሳምም መውለድ የሚያስችልሽን ህክምና
እያደረግሽ እያለ ባልሽ ከጀርባሽ ሌላ ሴትን እያወጣ ቢያስርግዛትስ?” ብላ ኒኪ
አይኗ በእምባ ተሞላ፡፡ “የሆነ ማታ ላይ የባልሽ አይፖድ ላይ እርጉዝ ሆዷን
የሚያሳይ የራቁት ፎቶን በኢ ሜይል ብትልክልሽስ? በቃ ህይወትሽ በሰከንድ
ውስጥ ግልብጥብጡ ቢወጣስ!?” አለቻት።

ግሬቸን በሰማችው ነገር በጣም ደንግጣ እና ሆዷ ታውኮ ሀሞቷ ሊወጣ እየታገላት ፍጥጥ ብላ ኒኪን አየቻት እና

“ሌንካ እርጉዝ ነበረች?”
ኒኪም መልስ ሳትመልስላት ዝም ብላ አይኗን አፍጥጣ ግሬቸንን ተመለከተች፡፡

ግሬቸንም “ግን እኮ ለሁላችንም የነገርሺን ከአደጋው በፊት ስለ እሷ ስምተሽ እንደማታውቂ ነበር።”

ኒኪ ራሷን ነቅንቃ ከድንዛዜዋ ወጣች እና ዝምታዋን ቀጠለች፡፡

“በኢየሱስ ሥም! ግን አንቺ ፎቶዎችን አይተሽ ነበር ስለ እሷም ታውቂ
ነበር ኒኪ?” ብላ ግሬቸን በፍርሃት ተንቀጠቀጠች፡፡

ምናልባት በአደጋው ውስጥ ኒኪ እጇ ይኖርበት ይሆን እንዴ? ብላ
ግሬቸን አሰበች፡፡

ተነስታ ለመሄድም እያመነታች እጇን ቦርሳዋ ላይ አስቀመጠች፡፡ ይህንን
ግሬቸንን ሁኔታ ያየችው ኒኪም ዶውግን አፈቅረዋለሁ። እሱ ላይ አንዳችም ክፋ ነገር አላደርግም:: እሱ ግን በጣም ነው ልቤን የሰበረው” ብላ አዘነች፡፡

“ግን ታውቂ ነበር?”

ኒኪ ራሷን በአወንታ ነቀነቀች፡፡

“ፎቶዎችንም አይተሻል? ሌንካ እርጉዝ ነበረች?”
“አዎ” አለቻት እና “
ከመሞቱ ከወር በፊት ነው ፎቶዎቹን ያየሁት::”ካለቻት በኋላ ማልቀስ ጀመረች፡፡

ግሬቸንም ወንበሯን አስጠግታ አቀፈቻትና “ለምን አልነገርሺኝም ያን ጊዜ የኔ ቆንጆ?”
“እንዴ ይሄ እኮ የሚያሳፍር ነገር ነው እንዴት ይነገራል?”
“እና ዶውግን ዝም አልሺው?”

“አውቃለሁ ዶውግን ከቤቴ ላባርረው እችል ነበር፡፡ ግን በቃ ትዳሩን ብሎ
ይመለሳል ብዬ ዝም አልኩኝ። ምንም ነገር እንዳላየሁ ሆኜ አሳለፍኩኝ::
ታውቂ አይደል ግሬች ዶውግ እኮ ዓለሜ ነው።”

“እንዴ የተረገዘው ልጅስ?”
“አላውቅም! ነገሩ እኮ ለእኔ አዲስ ነገር ነበር። ሁሉ ነገር እኮ በጣም ነበር ግራ ያጋባኝ የነበረው። እናም በመጨረሻ ምንም ሳላወራው ሞተብኝ።
በጣም ዘግይቼ ነበር።” ብላ ኒኪ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች።

ኒኪ አልቅሳ ከወጣላት በኋላ ለአንድ ሰዓት ያህል ሲያወሩ ቆዩ።
ግሬቸንም ለኒኪ ለምን ወደ ኒውዮርክ ሄደሽ አዲስ ህይወት አትጀምሪም?
ብላ ሀሳብ አቀረበችላት፣ እና ኒኪም እንደምታስብበት ነግራት ተለያዩ።

ኒኪ ለዓመት ያህል ውስጧን ሲያኝከው የነበረውን የሌንካን የእርግዝና
ጉዳይ ለግሬቸን ስላወራች ትንሽ ቀለል ብሏታል። መኪናዋን እያሽከረከረች
ወደ ቤቷ እየሄደች እያለችም ዴሪክ ዊሊያምስ ደወለላት።

መኪናዋን መንገድ ዳር ከሚገኝ የጃካራንዳ ዛፍ ስር አቆመች እና ስልኩን
ስፒከር ላይ አድርጋ ማውራት ጀመረች::
“ሄሎ ዴሪክ ባለፈው ለእኔ አስበህ መልዕክት ስለላክልኝ አመሰግናለሁ።
እቤት ከገባሁ በኋላ እንዳልደውልልህ...”

ኒኪ የግድ በቶሎ ዛሬ ማታ መገናኘት ይኖርብናል” አላት። ለመጀመሪያ
ጊዜ ድምፁ ውስጥ ፍርሃት እና አለመረጋጋትን ያስተዋለችው ኒኪም ምን
ሆኖ ነው እንደዚህ የፈራው? ለእኔ ነው ወይስ ለራሱ ነው የፈራው?' ብላ

“ምነው ችግር አለ እንዴ?” ብላ ጠየቀችው።

በሩሲያውያን እና በሮድሪጌዝ መካከል የሚደረገው የአደንዛዥ ዕፅ ጦርነት ቀላል አይደለም። ነገሩ እስከ ከተማው ማዘጋጃ ቤት ድረስ ይዘልቃል። መሉው የሎስ አንጀለስ ከተማ በዚህ የአደንዛዥ ዕፅ ቀለበት ውሰጥ ነው የሚገኘው።” አላት እና ስሜቱ የተረበሽ እና የፈራ መሆኑ
እየታወቀበትም ባንኮችና እና የበጎ አድራጊ ተቋማት ሁሉ የዚህን አደንዛዥ ዕፅ ገንዘብ በህግ ወጥ መንገድ ስለሚያዘዋውሩ ሁሉም የድርሻቸውን ያገኛሉ። አላት።

ኒኪም የዊሊያምስ አለመረጋጋት እና መፍራት ትንሽ አሳስቧት “እሺ ተረጋጋ። ከግድያው ጋር የሚገናኝ ነገር አግኝተሃል? ማለትም ግድያው ከእኔ ጋር ይገናኛል ?

“ምናልባት አዎን” ብሎ ሲመልስላት ኒኪ እርግጠኛ ለመሆን ብላ

“ስማቸውን ልትነግረኝ ትችላለህ?”

“አሁን በስልክ ልነግርሽ አልችልም።” ብሎ ዊሊያምስ በመቀጠልም “የሆነ ስወር ያለ ቦታ ከተገናኘን በኋላ ነው የምነግርሽ” አላት እና የሚገናኙበትን ሆቴል ተስማሙ::

“ስለ ሌንካስ ያገኘኸው ነገር አለ?” ብላ ኒኪ ጠየቀችው።

“አዎ አለ፤ የእሷም ነገር ከዚህ ጉዳይ ጋር ይያያዛል፡፡ እሱንም ስንገናኝ አወራሻለሁ።”

“በስልክ ልትነግረኝ አትችልም?” ብላ ኒኪ ተለማመጠችው፡፡ ስለ ጣውንቷ ለማወቅ ዓመት ፈጅቶባታል፤ እና ከዚህ በኋላ ለደቂቃ እንኳን መጠበቅ ስቃይ ነው የሚሆንባት

“አልችልም፡፡ አሁን ቤት ሄጄ ልብሶቼን በሻንጣ ማዘጋጀት አለብኝ
👍3😁1🤩1
አንቺም ብትሆኚ ስትመጪ ለቅያሪ የሚሆኑሽን ልብሶች በትንሽ ሻንጣ
አዘጋጂ። ሁለታችንም አደጋ ላይ ነን፡፡ ስለዚህ ለጥቂት ጊዜ ያህል ነገሮች
እስኪረጋጉ ድረስ ተደብቅን መቆየት ይኖርብናል።”

ኒኪ ብዙ ጥያቄ ልትጠይቀው ስትል ስልኩ ተዘግቷል። ይህ አይነት
ፍርሃትን በእሱ ላይ አይታ ባታውቅም ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ስለ ጣውንቷ
ማወቅ እንደምትችል ስታስብ ደስ አላት፡፡

ስለ ጣውንቴ ካወቅኩኝ በኋላ ንዴቴን ሁሉ ትቼ ከራሴ ጋር እታረቃለሁ ብላ በማሰብ ላይ እያለች ስልኳ ጮኸ፡፡

ስልኩን ስለማታውቀው ምናልባት ዴሪክ በሌላ ሲም የደወለላት መስሏት
በቶሎ ስልኩን አነሳች እና “ዴሪክ” አለችው፡፡

ከዚያኛው የስልክ መስመር ግን የሚመጣው ድምፅ በጣም በሰቆቃ
የተሞላ እና ፍፁም የሚረብሽ ድምፅ ነበር። ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን
የድምፁን ባለቤት ስታውቅ

“ይሄማ በፍፁም ሊሆን የማይችል ነገር ነው!”

“ዶክተር ሮበርትስ?” አላት ብራንዶን ግሮልሽ እና በማስከትልም “አንቺ
ነሽ?” ብሎ ጠየቃት፡፡

“አዎ ነኝ ብራንዶን” ብላው ልቧ በጣም እየደለቀባትም “የት ነው ያለኸው?”

“እርዳታሽ ያስፈልገኛል” ብሎ ሳግ አፈነው እና “ሊገድሉኝ ነው መሰለኝ
“አይዞህ እኔ አለሁልህ፡፡ ግን የት እንዳለህ ንገረኝ በመጀመሪያ

“እሺ” አለ እና በረዥሙ አየር ስቦ “እኔ... እኔ... ጥግ ላይ...”

ተናግሮ ሳይጨርስ የምት ድምፅ ተሰማት እና ስልኩ ተቋረጠ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ኒኪ ኤስ ኤል ኤስ ሆቴል ቁጭ ብላ ዴሪክ ዊሊያምስን እየጠበቀች
ትገኛለች:: ዴሪክ ዊሊያምስ እንደነገራትም በትንሽ ሻንጣ ልብስ ይዛ መጥታለች፡፡ ይህንን ደግሞ ያደረገችው በተለይ ብራንዶንን ካዋራችው በኋላ ነው። በተለይ ደግሞ አሰቃቂው ድምፁ ትንሽ እንድትፈራ እና ዊሊያምስ አድርጊ ያላትን ነገር እንድታደርግ አስገድዷታል። ብዙ ልብስ ይዛ አልመጣችም፡፡ ሮድሪጌዝ ከቤቷ እንዲያስወጣት አትፈልግም።
ስለ ብራንዶን ስትነግረው ምን ሊል ይችላል ብላ አሰበች። እያወራት
እያለ ስለ ስማችው የምት ድምፅ ትነግረውና ሀሳቡን እንዲያካፍላት
ትጠይቀዋለች፡፡ ይህንን ነገር ለፖሊሶች እስከ አሁን አላሳወቀችም።በመጀመሪያ ይህንን የብራንዶንን ነገር ለዊሊያምስ ነው ልትነግረው የፈለገችው::
ኒኪ ፈዘዝ ያለ ጥቁር ሱሪ ከአረንጓዴ ቦዲ ጋር አድርጋለች። ቦዲዋ አንገቱ ክፍት ስለሆነ የጡቷ መካፈቻ ከጡት ማስያዢያዋ አፈትልኮ ይታያል። ይህንን አይነት ልብስ ለብሳ የመጣችው ዴሪክ ዊሊያምስን ለማማለል ሳይሆን ስለ ጣውንቷ ስትስማ ፅድት ብላ ለብሳ መሆን እንዳለበት ወስና ነው። ልክ ከዶውግ አጠገብ ሁለቱ ቆመው የሚወዳደሩ ይመስል ዝንጥ ብላ ነው የመጣችው።

ሌንካ የወደፊት ህይወቷን ብቻ ሳይሆን ያበላሸችባት ከዶውግ ጋር
አብረው ያሳለፉትን ጥሩ የፍቅር ጊዜዎችን እና ትዝታውን ጭምር
እንዳታስብ አድርጋ ነው የነጠቀቻት። ለጓደኛዋ ግሬቸን የነገረችውን የሌንካን
እርግዝና ለዴሪክ ዊሊያምስ ለምን እንደደበቀችው አሁን ግልፅ ሆኖላታል።
የዚህ ምክንያቷ ደግሞ እሷ ታግላ ያልተሳካላትን ነገር ሌንካ እንደቀልድ
ማድረግ መቻሏ ነው። እሱም ልጅ ማርገዝ ነው። ሌንካ ለዶውግ ልጅ
አርግዛላታለች፡፡ ኒኪ ግን ልታረግዝለት አልቻለችም፡፡ ይሄ ደግሞ በጣም
አሳፍሯታል።

ኒኪ ግድግዳው ላይ ያለውን ሰዓት ስትመለከት ከምሽቱ 1፡22 ይላል፡፡
ዊሊያምስ ከቀጠሮው 22 ደቂቃ አሳልፏል። ይህ ደግሞ የዴሪክ ፀባይ
እንዳልሆነ ታውቃለች። ለማንኛውም ዛሬ የጣውንቷን ሌንካን ማንነትና ለምን ባሏ ከሌንካ ጋር የፍቅር ግንኙነት የመሰረተበትን ዋነኛ ምክንያትን
ታውቃለች፡፡ እና ዊሊያምስ እስኪመጣ ታግሳ መቆየት አያቅታትም።

አሁን ከምሽቱ 1፡30 ይላል ኒኪ ትዕግስቷ አለቀና ስልኳን አውጥታ
“የት ነው ያለኸው? በሰላም ነው?” የሚል መልዕክት ላከችለት።
ዴሪክ ዊሊያምስ ጠረጴዛው ላይ ያስቀመጠውን የስልኩን የንዝረት ድምፅ
ሲሰማ ገና ከመታጠቢያ ክፍሉ ወጥቶ ልብሱን ሊለብስ ነበር። ስልኩን
ሲመለከት የኒኪን መልዕክት አየ።

“እየመጣሁ ነው፡፡ ይቅርታ ስለዘገየሁ” የሚል መልዕክትን ላከላት። ኒኪም መልዕክቱ ሲደርሳት ትንሽ ተረጋጋችና ብርጭቆዋን አንስታ መጠጡን
ተጎነጨች፡፡

ዴሪክ ዊሊያምስ ማስታወሻ ለመፃፍና በኢሜይል ለሚያምነው ሰው ለመላክ ብዙ ጊዜ ፈጅቶበታል። የከተማው ከንቲባ ፎንቴስ የቀድሞ ፀሐፊ ከነበረችው ቲና ድሬይ ያገኘችው መረጃ በጣም አደገኛ እና ሁለቱንም ሊያስገድል የሚችል ነገር ነው:: እርግጥ ነው መረጃ ሀይል ነው፤ በዚያው ልክም መረጃ ህይወትን ሊያሳጣ እንደሚችል ያውቃል። እንደምንም ፅፎ
የጨረሰውን መረጃ ለጓደኛው አላን በ ኢ ሜይል ከላከለት በኋላ ላፕቶፑን
ዘግቶ ቦርሳው ውስጥ ከተተው:: ጫማውን እያሰረ እያለም ደውል ተደወለ፡፡

“አሁን ሊመጡ አይችሉም መቼስ? ማን ሊሆን ይችላል? እነዚያ የሎሬን
ጠበቃዎች ፍርድ ቤቱ የወሰነብኝን ክፍያ እንድፈፅም ሊነዝንዙኝ ይሆናል ወደ እዚህ የመጡት ብሎ እያሰበ ትንሽዬ የጉዞ ሻንጣውን በጀርባው አንግቶ ወደ በሩ ሄደና በሩን ሲከፍት በሩ ላይ የሚያውቀን ሰው ስለተመለከት ተገረመ::

ሰውዬውንም “ይቅርታ አሁን ጥሩ ሰዓት ላይ አልመጣህም፡፡ እኔ አሁን
በጣም እቸኩላለሁ.…” ብሎ ተናግሮ ሳይጨርስ ስውዬው በመጀሪያው ጥይት
የዊሊያምስን አናት ነደለው፡፡ ቀጥሎም ሁለት ጥይቶችን በደረቱ ለቀቀበትና
የቤቱ ወለል ላይ ሲወድቅ ትቶት ወጣ።

ኒኪ ከዚህ በኋላ ዊሊያምስ የቀጠሮው ቦታ ላይ እንደማይመጣ አውቃለች። ስለዚህ ሦስት አማራጮች አሏት። የመጀመሪያው አማራጫ ዊሊያምስ እንደነገራት ከዚህ ከተማ ርቃ የሆነ ሆቴል ውስጥ ተደብቃ ዊሊያምስ እስኪደውልላት ድረስ መጠበቅ ነው፡፡

ሁለተኛው አማራጫ ደግሞ በቀጥታ ወደ ቤቷ መመለስ ነው።

ሦስተኛዋ አማራጭ ደግሞ ዝም ብሎ መጠጣት ነው፡፡

ኒኪ ስለ ሊዛ እና ትሬይ ግድያ፣ ስለ ሮድሪጌዝ የአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር
እናም ደግሞ ስለ ማዘጋጃ ቤት ባለስልጣኖች የሙስና ወንጀል ደንታ
የላትም፡፡ እሷ በጣም ጓጉታ የመጣችው ስለ ሌንካ ለመስማት እና እፎይ
ብላም ከንዴቷ መገላገል ነበር። ግን አልሆነም፡፡ የቋመጠችለትን የሌንካን
ነገር አሁን መስማት አልቻለችም፡፡ ምናልባትም ለወደፊቱ ጭምር አትሰማ
ይሆናል፡፡

ስለዚህ ሦስተኛ ምርጫዋን መረጠች እና መጠጣት ጀመረች።

ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ ኒኪን ባር ማኑ ቀሰቀሳት እና “መኝታ ላስይዝልሽ፡፡ የእኔ እመቤት” ብሎ ጠየቃት፡፡
“ችግር የለውም እኔ አስይዛታለሁ።” ብሎ ከጎኗ ከሚገኘው ወንበር ወደ እሷ ጠረጴዛ ተሻገረ እና ለባር ማኑ ክሬዲት ካርዱን እየሰጠው “ደብል ስፔራሶ እና አንድ ብርጭቆ በረዶ የሌለው ውሃ አቅርብላት” አለው፡፡

“እሺ ጌታዬ” ብሎ ባርማኑ ከአጠገባቸው ሄደ እና ብቻቸውን ቀሩ፡፡

ኒኪም ከፊት ለፊቷ የተቀመጠው ሰው ፊት ሁለት እየሆነ ስላስቸገራት እና ጉድማንን እና ዴሪክን መለየት አቅቷት በጣቷ ደረቱን እየመታች አንተ ዴሪክ አይደለህም አይደል?” “አዎን አደለሁም” አላት፡፡

“ዴሪክ እኮ አልመጣም:: ቀጠሮ ይዘን ነበር። አንተ ለምን መጣህ?አሁንም ትከታተለኛለህ ማለት ነው?” ብላ በስካር አንደበት ተናገረችው::

ኒኪ ነቅተሽ አዳምጪኝ” አላት፡፡

ይሄኔም ያዘዘው ኤስፔሪሶ መጣለት።

ኒኪም ትኩሱን ኤስፔሪሶ አንስታ
ቶሎ ቶሎ ጠጥታ ጨረሰች:: እና በትንሹ ነቃች፡፡

ሚኪ ነቃ ብለሽ አዳምጪኝ፡፡ መጥፎ ዜና አለኝ፡፡ ዴሪክ ዊሊያምስ ሞቷል። “አላት፡፡

“ምን? ዛሬ ማታ እኮ ሜሴጅ ተላልከን ነበር፡፡”

“መቼ?”

“አሁን ምሽቱን” ብላ ኒኪ የሞባይል ሰዓቷን አይታም “ከሦስት ሰዓት
👍2
በፊት ነው።”

ጉድማን ስልኳን ተቀበላት እና የተላላኩትን ሜሴጅ አይቶ እየመለሰላት
“አዎን ላንቺ ሜሴጁን ከላከ በኋላ ነው አፓርታማው ውስጥ የተገደለው።
አንድ ጊዜ ግምባሩን፣ ሁለት ጊዜ ደግሞ ደረቱን በጥይት ተመትቶ ነው ህይወቱ ያለፈው:: ሽጉጡ ላይ ሳይለንሰር ተገጥሞለት ስለነበር የሽጉጡን
ድምፅ ጎረቤቶቹ አልሰሙም::” አላት።
ኒኪ ከዚያ በኋላ የጉድማን ከንፈር ሲንቀሳቀስ ታያለች እንጂ የሚያወራው ነገር አይሰማትም: “ምስኪን ዴሪክ በጣም ጥሩ ሰው ነበር እኮ፡፡ በቃ ለእኔ እውነትን ለማውጣት ብሎ ነው እኮ ህይወቱን ያጣው” እያለች ቡዝዝ ብላ ብርጭቆው ላይ የሚንሳፈፈውን ሎሚ መመልከቷን ቀጠለች::

ጉድማንም ትከሻዋን ይዞ እየነቀነቀ ሚክ እባክሽን ዴሪክ ምን ሊነግርሽ ነበር የቀጠረሽ?” አላት፡፡ ስለ ሌንካ ነበር ሊነግረኝ የነበረው::” አለችው፡፡

“ስለ ባልሽ ውሽማ? ስለ እርግዝናዋ ነበር ሊነግርሽ የነበረው?”

ኒኪም የግርምት ፊት እያሳየችው “ታውቅ ነበር ማለት ነው?”

“አዎን ጆንሰን ነው መረጃውን ያገኘው፡፡ ግን ለምን ደበቅሺን?”

“አልደበቅኳችሁም ግን በቃ መናገር አልፈለግኩም:: ደግሞም ሁሉ
ነገሬን ለእናንተ የግድ መናገር አለብኝ እንዴ?” አለችው ተኮሳትራ::

“እንደሱ ማለቴ አይደለም። ነገር ግን ምናልባት ግድያዎቹ ከእሱ አደጋ
ጋር ሊገናኙ ስለሚችሉ ነው::” አላት፡፡

ኒኪም ትከሻዋን ሰብቃ ዝም አለችው::

ጉድማን በጣም ትዕግስት ባጣ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ እየተመለከታት
“ዴሪክም አንቺም የጉዞ ሻንጣ ይዛችኋል፡፡ ከተገናኛችሁ በኋላ ወዴች ልትሄዱ ነበር?” ብሎ ጠየቃት፡፡

“አንድ ላይ አይደለም የምንሄደው። ከተገናኘን እና ካወራን በኋላ ተለያይተን ለመሄድ ነበር ዕቅዳችን፡ ዴሪክ እኛ እዚህ ከቆየን ኣደን እንደሚገጥመን ጭምር ነው ያስጠነቀቀኝ እና ከዚህ መሸሽ እንደሚኖርብን ነበር ያስጠነቀቀኝ። ግን ምን ያደርጋል አሁን ዴሪክ የፈራው ደርሶበታል”

“ከማን ነበር የምትሸሹት? ሥም እፈልጋለሁ። ንገሪኝ” አላት እየጮኸባት፡፡

ኒኪ ግን መልስ ከመመለስ ይልቅ ዝም ስላለቺው ጉድማን ከንፈሯን
በሀይል ሳማት። እሷ ግን በድን ሆና ምንም የመሳም ምላሽ አልሰጠችውም።
የዴሪክ ዊሊያምስ ሞት ይህንን ስሜቷን አጥፍቶባታል። ከዚያ በኋላ ኒክ ስለ
ሮድሪጌዝ፣ ስለ ማዘጋጃ ቤት ሙሰኞች፣ ስለ ዊሊ ባደን እና ስለ የተለያዩ
ባንኮች የአደንዛዥ ዕፁን ገንዘብ የማስተላለፍ ሁኔታን ጭምር ልክ ዴሪክ
ዊሊያምስ ፅንስ ሀሳቡን በገለፀላት መልኩ ገለፀችለት።

ጉድማንም የተለያየ ጥያቄን ሲጠይቃት ቆይቶ በቂ ነው የሚለውን መልስ ካገኘ በኋላ ሻንጣዋን በእጁ ይዞ ተነሳ፡፡

“እኔ ነኝ ቤት የምወስድሽ፡፡” አላት፡፡
“ቤት መሄድ አልችልም አደጋ ሊኖረው ይችላል” አለችው፡፡
እሱም “ያንቺ ቤት ሳይሆን የእኔ ቤት ነው የምወስድሽ” አላት።
ኒኪም ከእሱ ጋር ህይወት መስርታ ብትኖር ምን አይነት ድንቅ ነገር
ሊሆንላት እንደሚችል በአዕምሮዋ ሳለች። ማለትም ሲንከባከባት እና ከማንም
ሰላይ መከታ ሲሆናት በውስጧ ስትስል ቆይታ ነገሩ ሊሆን እንደማይችል
ገባት::
ከተቀመጠችበት ተንስታም ከንፈሩን በስሜት ከሳመችው በኋላ “በጣም
ጣፋጭ ስው ነህ፡፡ ግን ከአንተ ጋር አብረን ልንሆን አንችልም::”

“ለምን?”

“ምክንያቱም ልቤን ለዶውግ ሙሉ በሙሉ ሰጥቼው ነበር፡፡ እሱ ግን
እንዳይመለስ አድርጎ ልቤን ሰብሮታል።” ብላው ሻንጣዋን ተቀብላው ከሆቴሉ
ወጣች::

ይቀጥላል
👍2
አትሮኖስ pinned «#የፍቅር_ሰመመን ፡ ፡ #ክፍል_አርባ_ስድስት ፡ ፡ #ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን ፡ ፡ #ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው ...ከኮሪያውያን የፍል ውሃ ቦታ ወጡ እና ወደ ሱሺ ባራቸው አመሩ፡፡ ሱሺ ባር ውስጥም ተቀምጠው እየበሉ እያሉ ግሬቸን “ይህንን ቀጠርኩት ያልሺውን የግል መርማሪሽን ከየት ነው ያገኘሽው?” ብላ ኒኪን ጠየቀቻት፡፡ ኒኪም “ከጎግል ላይ ነው:: ስለ እሱም በደንብ አድርጌ ካነበብኩኝ በኋላ ነው…»
#የወድያነሽ


#ክፍል_ስድስት


#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል


አንዳንድ ቀን አካባቢውን መልከትከት ብዩ ሰው ያለመኖሩን አረጋግጥና ሥጋዊ ስሜቷን ለመቀስቀስ የሚችለውን የአካላቷን ክፍል ከፍ ወይም ዝቅ ብዬ
መደባበስና መጎነታተል አዘወተርኩ፡፡ ከወደ ውስጥ እየጋፈረ የሚያጠልማት
የኃፍረቷ ጎርፍ አፏን አፍና የሣቋን ግፊት እንድታምቅ ያስገድዳታል። ፊቷን
ሽፍና መሽኮርመምና ሰብሰብ ብላ መቀመጥ የዘወትር ልማዷ ነበር፡፡ እንደ ዘበት ሽብ ያደረገችውን ሻሿን ድንገት ስቤ እይዝና ያንን ውብ ኑግ መሳይ ጸጉር
በታትኖ ማየት ወደ እርሷ ከሚስቡኝ ሁኔታዎች ሁሉ የበላይነትን ያዘ፡፡

እንድ ቀን እንደ ልማዴ የጊዜና የአካባቢውን ሁኔታ ተመልክቼ እጅዋን
እያልመዘሙዝኩ አፌን ለወሬ ሾል ሾል ሳደርግ “ዋ" እለችኝና ዐይኔን እያየች
እናትዎ ያዩዎትና አጉል ቅሊት ይቀልላሉ፡ የኔ እንደሁ ዕውቅ ነው፡ ያው ሂጂ
ውጪ ከቤቴ ብለው ማባረር ነው» ብላ የተሰደሩ ጥርሶቿን ፈልቅቃ አስጐበኘችኝ፡፡ ለወጉ ያህል ጥቂት ተላፋን፡፡ ልባችን ተቀራርቦ ስሜታችን ይበልጥ ተዋሐደ፡፡ በፍቅራዊ ስሜት ለሚከታተሏት ዐይኖቼ የምትሰጠው ምላሽ አርኪ በመሆኑ የፍቅራችን ጋቢ ዐርቡ እየሰፋ ሒደ፡፡

እሑድ ጠዋት ነበር። ወላጆቼ የውብነሽን አስከትለው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔደዋል፡፡ እናቴ ስለ እኔ ወደ ቤተ ክርስቲያን ያለመሔድ ስትናገር
«የሱን ነገር ተዉኝ! የእናንተ ጸሎት ለሁላችንም ይበቃል” ይላል። አይጣል
እቴ! ይኸስ የጤናም አይደል» ትላለች፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ የምታቀርበውን
ነቀፌታ ከጉዳይም አልቆጥረው:: ተኝቼ አረፈድኩ፡፡ ጋቢ ለብሼ የመኝታ ቤቴን
በር ስከፍት የወዲያነሽ አረንጓዴ የውስጥ ልብስ ብቻ ለብሳ እንግዳ መቀበያ
ክፍል ውስጥ መወልወያ ጨርቅ ይዛ ቆማለች፡፡ ጸጉሯ በተንተን ብሉ በአንገቷ
ዙሪያ ተሽመልምሉ ይዘናከታል፡፡

የአካላቷ ሙላት የመጨረሻውን ደረጃ ይዟል። ያ ከዓመት በፊት በርኅራኄና በአኗኗሯ በዐዘኔታ ላይ ተመሥርቶ የነበረው ስሜቴ ፍጹም ተለውጦ
አሁን ወደ ልዩ ሥጋዊ ውዴታ አጋድሏል፡፡ ዛሬ በተለይ በልቤ ውስጥ የጉርምስና
ደም ተንሽከሽከ፡፡

በትዕዛዛዊ አቀራረብ ሳይሆን ልዩ የመቀራረብን ስሜት ለማብሠር
በምታስችል ለስላሳ ድምፅ "ነይ እስኪ የወዲያነሽ?» ብዬ ጠራኋትና አልጋው
ጫፍ ላይ ተቀመጥኩ። የመስታወት መወልወያዋን እንደ ያዘች በአለባበሷ አፍራ መዝጊያው አጠገብ ቆመች። ስልክክ ባለው ጠይም ፊቷ ላይ ወርዶ ከጉንጫ ላይ ሲደርስ የሚርመሰመሰው የወጣትነት ሙሉ ደም ግባቷ የምሆነውን አሳጣኝ፡፡

«ግቢ እንጂ ምን ያስፈራሻል?» ብዩ ለማግባባት ሞከርኩ። ዐፈር ከድቷት እንደ ዘመመች የድሃ ጎጆ አንገቷን ወደ ግራ ጎን ሰበር አድርጋ ቆመች።

እንደገና ነይ እንጂ ግቢ የወዲያነሽ» ብዩ አባበልኳት። ውስጥ ውስጡን የበላይዋና አዛዥ መሆኔ ስለ ተሰማት በፍርሃት እየተናጠች ገባች፡፡ በሩን ዘጋሁት። ደነገጠች። የፈገግታዋ ንጋት ቀስ በቀስ ጠለሰ። እንደሚንበረከክ ተማሪ ጉልበቷን ሰበር አድርጋ ወለሉ ላይ ተቀመጠች፡፡ እኔም ስለ ወለሉ ላይ ትቢያ ምንም ሳልጨነቅ ከፊት ለፊቷ ቁጭ አልኩ፡፡ በስሜት ተቁነጠነጥኩ፡፡ ቤቱና በቤት ውስጥ ያለው ዕቃ ሁሉ «መጡብህ! ደረሱብህ! የሚሉኝ ስለ መሰለኝ ዐይኖቼ ቃበዙ፡፡ ድንገት ብድግ ብዬ «ተነሽ» አልኳት፡፡ አነጋገሬ ቁጣ ቅልቅል በመምሰሉ ወዲያው ተነሣች። ልፊያ ቢጤ ለመጀመር በማሰቤ ሽንጧ ላይ ነካኋት። ተሸማቀቀች። ታዲያ ምን ያደርጋል፡ ምን እንደምፈልግና እንደማደርግ መላ ቅጡ ጠፋኝ፡ መላ አካላቴ ብው ብሎ ጋለና ፍርሃቴን ገፈፈው፡፡ የለበስኩት ጋቢ ተንሸራትቶ እግሬ ሥር ወደቀና በእግራችን ረጋገጥነው። እጆቼን ባንገቷ ዙሪያ ጠምጥሜ በልዩ ደስታ እምነሽነሽ ስለ ነበር የወደቀውን ጋቢ ቁብም አላልኩት። ድንገት አፈትልካ ለመሄድ ሞከረች::
አልተሳካላትም፡፡ ፊቷን ወደ ተዘጋው በር አዙራ ተቀመጠች፡፡ ከበስተጀርባዋ ቆሜ
ጎንበስ አልኩና እጄን በትከሻዋ አኳያ ወደፊት ቁልቁል ሰደድኩት። እንደገና
ከፊት ለፊቷ ዞሬ ተንበረከከሁ፡፡

ሳትወድ በግድ በአገጯ ወደ ላይ ይዤ ፊቷን አየሁት። እንባዋ ይጎርፋል፡፡ በእጄ ስቢያት ተነሣሁ፡፡ «እኔ እኮ የቀልዴን ነው:: ደስ ይልሽ እንደሆን ብዩ ነው እንጂ ደስ የማይልሽ ከሆነማ ከዛሬ ጀምሮ ከደረስሽበትም አልደርስ እ! » ብዬ እጆቿን እንደ ያዝኩ ዝምታዬን ተጎናፀፍኩ። ለማስመሰል እንጂ ከልቤ አልነበረም፡፡ ተፋጠጥን፡፡ ዐይኖቼ ቦዙ። ዘንጉን በዳበሳ እንደሚፈልግ ዐይነ ሥውር እጆቿን ዘርግታ አንገቴ ላይ ተጠመጠመች፡፡ ደረቴ ላይ ተለጥፋ አገጬ ስር ከቀረቀረች፡፡ የፊቷ ትኩሳትና የደረቷ ሙቀት ሲገናኙ ኃይለኛ ነዛሪ
የርካታ ማዕበል አጥለቀለቀኝ፡፡ የተስተካከለ ንዝረት ግን አልነበረም፡፡ ደረቴ ላይ እንደ ተለከፈች በጉንጯ ላይ እያቋረጠ የሚወርደው እንባዋ ስሷን ልብሴን አረጠባት። አዲስ ሰመመናዊ ቆይታ ተጀመረ፡፡ ከከንዲት ሥር ላይ የበቀሉ መንታ መቃዎች መስልን። ፀጥ እና ቀጥ በማለታችን እካባቢውን ጸጥታ
ሰፈነበት።

ግድግዳው ላይ የተንጠለጠለው ገደ ቢስ ሰዓት ጥበባዊ ተግባሩን ለመፈጸም ደወለ፡፡ እኔና እርሷም በዚያቹ ቅፅበት ከሰመመናችን ባነንን፡፡ ከራሷ ቀና ብላ በእንባ የተከበቡ ዐይኖቿን እና ፊቷን አሳየችኝ::

የስሜቷ ዶፍ ተፍ እለ። በሰውነቴ ውስጥ ያለው ኃይል ተንጠፍጥፎ ያለቀ ይመስል እጆቼ ዛሉ፡፡ ቀስ በቀስ አየት ሳደርጋት ወለሉ ላይ የወደቀውን ጨርቅ ይዛ በዝግታ ወጥታ ሒደች:: ዐይኖቼ አብረዋት ተጓዙ፡፡ እኔም ወለሉ ላይ
ወድቆ ባቧራ የተልሞሰሞሰውን ጋቢ አራግፌ ወደ አልጋው ግርጌ ወረወርኩት።አልጋዩ ላይ ወጥቼ በጀርባዬ ተንጋለልኩ:: ተንጠራራሁ፡ አፋሸግሁ፥ እግሮቼን እያኮራመትኩ ዘረጋሁ። ጥልቅ ፍቅር በውስጤ ተፍለቀለቀች፡፡ የአልጋው ሽቦዎች እስኪያንሲያጢጡ ድረስ ተወራጨሁ፡፡ እንደገና ቀና ብዬ አልጋው መኻል ተቀመጥኩ፡፡በስተራስጌ በኩል በምስማር ላይ የተንጠለጠለውን ኮቴን ተንጠራርቼ አወረድኩና ከልብሲ ጋር የከረረ ጠብ ያለኝ ይመስል አሽቀንጥሪ ግድግዳው ላይ አላተምኩት፡፡ ከአልጋው ላይ እመር ብዩ ወርጄ የወዲያነሽ አጥባና ተኩሳ ያስቀመጠችልኝን ሱሪ ከሻንጣ አወጣሁ፡፡ አልጋው ጫፍ ላይ ተቀምጬ እግሮቼን ባንድ ጊዜ ቁልቁል በሱሪው አቆልቋይ ሰደድኳቸውና ቀጥ ብዩ ቆምኩ፡፡ በዙሪያዩ ያለው ነገር ሁሉ አዲስና እንግዳ ነገር መስሎ ታየኝ፡፡ ሰማያዊ ሸሚዝ ለብሼና ግራጫ ኮት ደርቤ ጸጉሬን ሳላስጥርና ያደረ ፊቴን ውሃ ሳላስነካ መሰስ አልኩ፡፡ወዴት እንደምሒድ አልወሰንኩም፡፡

ደረጃውን ወርጀ ግቢው መኻል ደረስኩ፡፡ የወዲያነሽ የሚያምር ቢጫ ቀሚስ ለብሳና ዐመድማ ሻሽ አስራ ማድ ቤቱ በራፍ አጠገብ ቆማ አየኋት፡፡በግራ እጅዋ አንድ ንጹሕ ነጭ ጭልፋ ይዛ ነበር፡፡ በዚያ ሰምቼ በማልጠግበው ድምጿ «እጅዎን ላስታጥብዎት መምጣቴ ነበር፥ ቁርስ አዘጋጅቻለሁ ቆዩ አትሒዱ» አለችኝ፡፡ በአድራጐቴ ሁሉ እንዳልተቀየመችና ቅር እንዳላላት በማወቄ ልቤ በደስታ እንደ ፈረሰኛ ጎርፍ ሽቅብ ዘለለች። ላሳየችኝ ብሩህ ገጽ የተከማቸ ፈገግታ ላኩና «ተመልሼ እመጣለሁ አዘጋጅተሽ ጠብቂኝ» ብያት ወጣሁ። የትምዋልኩ እንጂ እንዳባባሌ አልተመለስኩም፡፡

ቤተሰቡ በሞላ ስለ ሁለታችን የስሜት ቁርኝት የሚያቀው አንዳችም ነገር
አልነበረም፡፡ የአባቴ የዕረፍት ሰዓታት ሃይማኖት ነክ መጻሕፍትን ለማንበብና
ያንኑ የሕግ መጽሐፉን በመነዝነዝ ላይ ስለተመደቡ ለሌላ ጉዳይ የሚውል ጊዜ
አልነበረውም፡፡ እናቴም የተማረ ሰው፣ ዐዋቂ ነው እያለች በጣም ስለምትመጣብኝዐበእርሷ እምነትና ልማድ ከ«ገረድ» ጋር ይህን መሰለን ግን
👍3
ኙነት ይፈጽማል ብላ አልጠረጠረችም፡፡ ከሁሉም በላይ የጠቀመኝና ከመሳቀቅም ያዳነኝ ግን፣
«በማንኛውም ጊዜ ቢሆን ቤተሰቦቼ ባሉበት አካባቢ ሁሉ እንኳንስ ፈገግ ማለትና ቀና ብለሽ እንዳታይኝ» ብዬ መክሬያት ስለ ነበር ቃሌን አክብራ በፈቃደኝነቷ መዝለቋ ነበር፡፡

ጊዜው እየጨመረ በሄደ ቁጥር የሁለታችን ፅኑ ፍቅራዊ ግንኙነት እየሰፋ
መጐልመሱን ቀጠለ፡፡ ሰው ከሌለና ቤተሰቦቼ ራቅ ወዳለ ሥፍራ መሄዳቸው
ከተረጋገጠ መኝታ ቤት ድረስ ቀጥ ብላ ትመጣና ያለ አንዳች ፍርሃት ተጫውታ
መሄድን ተላመደችው:: አበባና ንብ ሆንን። ተጣጣምን፡፡ በልቤ ውስጥ የፍቅር
እውነተኛ ቡቃያ በቀለ፡፡ የቡቃያውም የሕይወት መስኖ የሚፈልቀው ከየወዲያነሽ የፍቅር ምንጭ ሆነ፡፡

አንድ ነገር በማበላሸቷም ይሆን ወይም በመስበሯ እናቴ ስትቆጣትና ግልፍ ብሏት ስትገሥጻት በማይና በምሰንበት ጊዜ ሁሉ ግልጽ ባልሆነ የአነጋገር ዘዴ እየተጠቀምኩ የውክልና ያህል ጥብቅና እቆምላት ጀመር።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የዕለቷ ፀሐይ የምዕራቡን አድማስ ነክታለች፡፡ አካባቢያችን በጨለማ
መጋረጃ ሊጋረድ ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ ቀርተዋል፡፡ አትክልቱ ውስት በመዘዋወር ላይ እንዳለሁ ከመጠያየም ዐልፎ ለከይን ያዘ፡፡ ያው ምክንያት ሆኖ ወደ ቤት ገብቼ መስኮት አጠገብ እንደ ተቀመጥኩ የምሽቱ ከዋከብት ብቅ ብቅ ማለት ጀመሩ። ከዋክብቱም፣ ትልቁ በትልቅነቱ ሲንቦለቦል፣ ትንሿም በዚያ በመጠኗ ትንተገተጋለች፡፡ ከወደ ሰሜን ፈጣንና ቀዝቃዛ ንፋስ እየተዥጎደጎደ ይነፍሳል። የተመሳሳዮቹ ዛፎች ቅርንጫፎች እርስ በእርሳቸው እየተሻሹ የትርምስ ልፊያ ይዘዋል። መታደል ነው። እነርሱ ዘንድ ፍርሃት ይሉኝታ የለ! ንፋሱ ለዘብ
ጠንከር እያለ ስለሚነፍስ ጸጥታና ውካታ ትንቅንቅ የገጠሙ መሰለ። ከሩቅ
ከቅርብ የሚታዩት ዛፎች በጨለማ ጥልቅ ውቅያኖስ ተወጠው እንደ ወራቢ
ይወዛወዛሉ።

በጨለማው ውስጥ የሚንዠቀዥቀው የከዋክብት ብርሃን በዕፅዋቱ መጠንና ቅርፅ ላይ ልዩ ኅብራዊ ትርኢት ሥሏል፡፡ ስሜቴ ስለ ተመሰቃቀለ ተንቆራጠጥኩ። ከመኝታ ቤት ወጥቼ እንግዳ መቀበያ ክፍል ገባሁ፡፡

የወዲያነሽና የውብነሽ ራት ለማቅረብ ተፍ ተፍ ይላሉ፡፡ የወዲያነሽ የእህቴን የአረማመድና አንዳንድ የሁኔታ ቄንጦች በመጠኑ አስተውላ በመቅሰሟ
ማራኪነቷ በጣም ጎላ፡፡ ከራት በኋላ እንደገና ተመልሼ መኝታ ቤት ገባሁ።
ከያዝኩት መጽሐፍ ላይ ገና አምስት ገጽ ያህል እንዳነበብኩ በሩ በዝግታ
ተከፈተ። የወዲያነሽ በእርጋታ ከገባች በኋላ ከትራስጌዬ አጠገብ ሁለት ነጫጭ
ጠርሙሶች ይዛ ወጣች፡፡ ደረጃዎቹን ወርዳ ስትጨርስ በመስኮቱ በኩል ብቅ ብዩ አየኋት። በሦስት ትልቅ ኮባዎች ከተከበበው ውሃ አጠገብ እንደ ደረሰች ጐንበስ ብላ አንዱን ጠርሙስ አስቀመጠችው::

የያዝኳትን 'የቀትር ጨለማ” እልባት አድርጌባት እንደ ዘበት ወጣሁ።
ከቤት ሲወጣ በመጀመሪያው ደረጃ ላይ ቆምኩ፡፡ ያሰብኩትን እንዳልፈጽምና
የፍላጐቴን ጥማት እንዳላረካ አንድ ነገር እክል ሆነብኝ፡፡

ማታ ማታ ደረጃ ስንወርድና ስንወጣ አልታየን አለ» ተብሎ ከሦስት ወር በፊት የተተከለው መብራት ግቢውን ወገግ ያለ ብርሃን ሰጥቶታል።

ደግነቱ የብርሃኑ ውጋገን ከሰሜን ምዕራብ እስከ ሰሜን ምሥራቅ ብቻ ይዘልቅና ከዚያ ወዲያ ያለውን ቦታ ጨለማ ያሶመስምበታል፡፡ ዕንጨት ላይ
የተመታችውን ማብሪያ - ማጥፊያ ሦስት ጊዜ አንቀቅጬ አንተገተግኋት፡፡

የተንጠለጠለችው መብራት በዕረተ ሞገድ የተነካካች ይመስል እንደ
ውድቅት እሳት ራቅ ቦግ እልም፣ ቦግ እልም አለች። ተፈጥሮም ድጋፍ እንድትሰጥ የታደመች ይመስል ኃይለኛና ፈጣን ነፍስ ባናት ባናቱ ነፈሰ፡፡ ይህም መብራቲቱ ተቃጥላ ወደመች ለማለት ከእኔው ሽር ጋር የሚሰምር ምክንያት ሆነ።

ደረጃውን ገመሬ እንደ ለቀቀው ናዴ ተንደርድሬ ወረድኩት።የአወራረዱ ፍጥነት ስሕተት ነበር፡፡ ከዚያም በጣም ዝግ እያልኩና በጢሻ ውስጥ እያደባ እንደሚሽሎከሎክ አዳኝ እየተራመድኩ ከትልቁ ኮባ ጀርባ ቆምኩ።

ትንፋሼን ውጬ እያሰላሁ ከተጠጋሁ በኋላ ከበስተኋላዋ ዐይኖቿን
በጣቶቼ ሽፈንኳቸው። ባልተጠነቀቀው አካሏ ላይ ያረፉት ጣቶቼ ድንገተኛ
ድንጋጤ ፈጠሩባት፡፡

በቀጭን የድንጋጤ ድምዕ «ዋይ» ብላ ጮኸችና እኔ መሆኔን እንዳታውቅብኝ ድምፄን አጎርንኜ «ማን ነኝ? እስኪ ዕወቂኝ?» ብዬ ጠየቅኋት።

ምንም ቢሆን የውጪ ሰው አይሆንም በማለት ተረጋጋች፡፡ ሁለቱንም በውሃ የሞሉ ጠርሙሶች በአንድ እጅዋ ከሆድዋ ላይ ኣጣብቃ ከያዘች በኋላ የውሃ
ፍንጥቅጣቂ ባለባቸው የቀኝ እጅ ጣቶቿ የቀኝ ክንዴንና ጣቶቼን ዳበሰቻቸው።
የማወቂያ ምልክትና ዘዴ አጣች፡፡ እጅዋ ሌላውን እጄን ፍለጋ ሄደ። ግራ እጄን
ያዘችው:: ሰዓቴን አገኘቻት፡፡ በደስታ የተሽሞነሞነ ሣቅና ትንፋሽ አደባልቃ
ለቀቀች፡፡ «አሁንስ ዐውቄዎታለሁ፤ እርስዎ ነዎት» ብላ በረጅሙ ተነፈሰች።
ለቀቅኋት። ጠርሙሶቹን እግሯ ሥር ስታስቀምጥ እንደኛዋ ጠርሙስ ተከነበለች።

የወዲያነሽ በዚያች ሰዓት የሾመችው ጋን ቢተረተርም ግድ የላትም ነበር። ፊት ለፊቴ ቆመች፡፡ ውጋገን ያረፈበት የሚመስለው ጠይም ፊቷ የጨለማው ጥቁረት ይታገለዋል፡፡ የጨለማው ውስጥ ውበቷ እንጎሌ ውስጥ ተርከፈከፈ፡፡ የተጠሙት ዐይኖቼ በመመልከቻ ዋንጫቸው እየደነበቁ ጠጧት። ግን ቀመሱ እንጂ አልጠገቡምና ቦግ ብለው ተከፈቱ፡፡ በቀኝ እጅዋ እየሳብኩ ወደ ጓሮ ይዣት ዞርኩ፡፡ ማታ ማታ የትልቁ ቤት ጥላና የየዛፎቹ ውስብስብ ቅርንጫፎች የምድረ ግቢውን ደቡባዊ ክፍልና አካባቢውን ለየት ያለ ድፍርስ ጨለማው ይጥለብታል።

ተስካር ለመብላት እንደሚገሰግሱ ዲያቆናት ተመራርተን በስተደቡብ
በሚገኘው የግንብ አጥር ደረስን፡፡ በእኔና በእርሷ ሕሊና ውስጥ ሲፍለክለክ የቆየው
የፍቅር ስውር ኣካል ተጨባጭ ሕይወት ሆኖ ተከሠተ፡፡

እጆቼ አንገቷ ላይ ሲጠመጠሙ እጆቿ በወገቤ ዙሪያ እንደ ዝናር ዞሩ፡፡
" እንዲያ ሲሳብና ሲዥጎደጎድ የቆየው ነፋስ አቅጣጫውን ያስለወጡት ይመስል
ደብዛው ጠፋ፡፡ እንዲያውም አልአፍ የምትመጣ ደካማ ትንፋሽ መሰለ፡፡
በአቅራቢያችን ያለችው ኮካ ለጋ ቅርንጫፎች ደፋ ቀና እያሉ እርስ በእርሳቸው እየተሳሳሙ ይበተናሉ፡፡ ጉንጯ ላይ ሳም ሳደርጋት የፍቅር ደማቅ ችቦ ተለኮሰ አፌን ወደጎን አንሸራትቼ የከንፈሮቼን ነዲድ ከከንፎሮቿ አርኪ ገለት
በማጋጠም ምጣድና ክንባሉ ሆንን፡፡
በሕሊናችንም ውስጥ ያ የፍቅር ችቦ ፏ
ብሉ ሲቀጣጠል ታየኝ።

💫ይቀጥላል💫
👍4
#እንግዳ

በበጋ ወቅት ዝናብ በድንገት ቢመጣ፣
በሃምሌው ጉም መሃል ፀሃይዋ ብትወጣ
በቁርና በውርጭ ሃሩሩ ቢያስጨንቅ፣
በብርድ ቢጨበጡ በሃይለኛው ወበቅ፣
ድንገት ከተፍ ቢል ሁሉም ሳይጠበቅ፣
እንግዳ ይባላል ያለ ወቅቱ መጥቶ፣
አንድም ቀደም ብሎ አለያም ዘግይቶ፡፡
ታዲያ ዛሬ ዛሬ

ልብን ልብ ሲነሳ ቀልብ ሲያስት የኖረው፣
የህልም አለሙ እንጀራ የማይጠገበው፣
የአንጀት አንጀተኛ ስለት የማይለየው
በልብ ውስጥ ተቀብሮ በድብቁ ጓዳ፣
በድንገት ሲከሰት ልክ እንደ ዱብ ዕዳ፣
የተፈታ ህልም እንጂ ማን ሊለው እንግዳ፡፡


🔘ሻለቃ ወይን ሐረገ በቀለ🔘
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_አርባ_ሰባት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው


....አኔ ቤታማን እምባዋ እና የሚዘንበው ዝናብ መንገዱን እየጋረደባት መኪናዋን በደንብ እንዳታሽከረክር እያደረጋት ነው:: ግንቦት ላይ ሎስ አንጀለስ ውስጥ አይዘንብም ነበር፡፡ ግን የእሷን ስሜት ለማጀብ በሚመስል መልኩ ሰማዩም አብሯት እዬዬ እያለ ነው። አሁን እሷ ሰው ነው የሚያስፈልጋት። ውስጧ በጣም ሀዘን እና ተስፋ መቁረጥ እንደተሞላባት
ነው:: ስለዚህም ኒኪ ታስፈልጋታለች። ኒኪ የምትሰጣት አድናቆትን እና
ይቅርታን ለምዳዋለች። ልክ ሉዊስ ባሏ ያደርግላት የነበረውን ነገር ነው ኒኪ
የምታደርግላት እና ወደ ኒኪ መሄድ ይኖርባታል።

ዛሬ ማታ ነው እንግዲህ ለኒኪ ስትነግራት የነበረውን፣ ሉዊስ አይተወኝም የምትለው ነገር የተገላቢጦሽ መሆኑ የታወቃት። ባለፈው ማታ ሉዊስ ከፕሮግራሙ ላይ ሲቀር ነበር ከእሱ ጋር ያላት ግንኙነትን ማብቃት እንዳለበት ውሳኔ ላይ መድረስ የሚኖርባት።

አኔ የኒኪ ቤት ስትደርስ ዝናቡ ሀይሉን ቢቀንስም የመኪናው ጣራ ላይ
የሚያርፈው የዝናቡ ድምፅ ግን ይሰማታል። ከመኪናዋ ወርዳ የኒኪን ግቢ
ስትመለከት መኪናዋን ግቢ ውስጥ ስላገኘችው ኒኪ ቤት እንዳለች ለማወቅ
ቻለች:: ዝናቡ የእንጨት በሩን ስላረጠበው ነው መሰል በቀላሉ ቀጫጭን ጣቶቿን አሾልካ በሩን ከፈተችና ወደ ውስጥ ገባች፡፡

የኒኪ ቤት ሙሉ በሙሉ በጭለማ ተውጧል። ስለዚህም ኒኪ ተኝታ
ሊሆን ይችላል ብላ አስባ እንዳትረብሻት ብላ ልትመለስ ስትል ውስጧ እዚህ
ድረስ መጥተሻል እና ኒኪን ሳታገኚያት መመለስ የለብሽም አላት፡፡

በሩን ልታንኳኳ ስትል ግን ሀይለኛ የለቅሶ ድምፅ ሰማች፡፡ ድምፁ የሚመጣው ከጓሮ በኩል ስለሆነም አኔ እንዳትወድቅ ተጠንቅቃ በአጥሩ እና በቤቱ መሀል ባለው ክፍት ቦታ ወደ ጓሮ አመራች::

አየቻት፡፡ ወደ ኒኪ እየቀረበች ስትሄድም ኒኪ አይኗን ጨፍና እና ትንሽ
ጓሮው ጋር ስትደርስም ኒኪ ከአንድ ጃካራንዳ ዛፍ ሥር ተንበርክካ አየቻት። ወደ ኒኪ እየቀረበች ስትሄድም ኒኪ አይኗን ጨፍና እና ትንሽ ሽጉጥ ከጉሮሮዋ በኩል ወደ ላይ እንደ ደቀነች ተመለከተች እና በጣም ደነገጠች፡፡

ኒኪ እኔ ነኝ አኔ ነኝ!” ብላ ከዝናቡ ድምፅ በላይ በመጮህ ወደ ኒኪ እየሮጠች ሄደች፡፡ ኒኪም ድምፁን ሰምታ አይኗን ስትገልጥ አኔን በዝናቡ በስብሳ አጠገቧ ቆማ አየቻት፡፡

ለጥቂት ሰከንዶች ያህል ሁለቱ ዝም ብለው ሲተያዩ ከቆዩ በኋላም ኒኪ
ነይ ወደ ውስጥ ግቢ እና በዝናብ የበሰበሰውን ልብስሽን ቀይሪ” ብላት ይዛት ወደ ቤቱ ውስጥ ገባች፡፡

ከሰላሳ ደቂቃ በኋላ ኒኪ ብርድ ልብስ ለብሳ ሶፋ ላይ እንደ ህፃን ለጥ ብላለች፡፡ ዶውግ እና እሷ ልጅ ነበር ይፈልጉ የነበሩት። በመሆኑም ለመውለድ ያስችላት የነበረው ህክምና ሳይሳካለት ሲቀር ያለመውለድን እንደ ትልቅ ሀዘን ነበር የቆጠረችው፡፡ ግን በተደጋጋሚ ከደረሱባት ሀዘኖች በኋላ ትልቅ ሀዘን ምን ማለት እንደሆነ ገባት።

ምናልባት አኔ ባትመጣ ኖሮ ቃታውን ስቤ ራሴን አጠፋ ነበር? ብላ ራሷን ጠየቀች፡፡ ምናልባትም አኔ በእግዚአብሔር የተላከች መልአኳ ሆና ህይወቷን ታድጋዋለች፡፡

“ምናልባት አኔን የላከልኝ ከሞት ባሻገር የሚገኘው ዶውግ ባሌ ይሆን?'
የሚለው ሀሳብ ደግሞ ጥሩ ስሜትን ስለሰጣት ደስ አላት::

ዛሬ መሞት አትፈልግም። በፍፁም! ከዚህ በኋላ ብዙ የምታከናውናቸው ነገሮች ስላሏት ቢያንስ እነዚህን ነገሮች ካከናወነች በኋላ ምናልባት ሞቷን
ትፈልግ ይሆናል፡፡ አሁን ግን ቢያንስ ዴሪክ ያገኘውን እውነት እስክታውቅ ድረስ በህይወት መቆየት አለባት፡፡

ከኒኪ ቤት በትንሽ ርቀት ላይ ከቆመው መኪና ውስጥ የሚገኝ አንድ ሰው በጎግል መነጽሩ ወደ ኒኪ መኖሪያ ቤት ሲመለከት ቆየና መነፅሩን አውርዶ የመኪናው ዳሽ ቦርድ ላይ አስቀመጠው።

“በቅርቡ ሁሉ ነገር ይስተካከላል” ብሎም ለራሱ አጉረመረመ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ጉድማን ከዳየርስ ሆቴል የጎጆ ቤት ማረፊያ ቁጭ ብሎ እያሰበ ይገኛል።
ወደዚህ የመጡት በዴሪክ ዊሊያምስ ሞት ግድያ ላይ የፎሬንሲክ ምርመራ
የሚያደርጉ ባለሙያዎችን ውጤት ለማወቅ ነው:: ባልደረባው ጉድማን ከሃያ
ደቂቃ በፊት የጠጣው ቡና ስላልተስማማው ለሦስተኛ ጊዜ ሽንት ቤት ገብቶ እያማጠ ነው:: ሌሊት 11 ሰዓት ላይ ኒኪ የላከችለትን ኢ ሜይል ስልኩን ከፍቶ በድጋሚ ማንበብ ጀመረ::

“ሌሊቱን በሙሉ ሳስብበት ነው ያደርኩት። አሁን ዴሪክ ዊሊያምስ በህይወት የለም። ይህንን ነገር ላንተ መንገር ሳይኖርብኝ አይቀርም፡፡ብራንዶን ግሮልሽ ትላንትና ማታ በጣም በከፍተኛ ፍርሃት እና ጭንቀት ውስጥ ሆኖ ደውሎልኝ ነበር። ስለ ግሮልሽ ዋሽቻለሁ፡፡ አዎን ብራንዶን
ግሮልሽን ከዚህ በፊት አውቀው ነበር፡፡ እሱ ከዚህ ግድያ ጋር ይያዝ አይያዝ
የማውቀው ነገር የለም” የሚል መልዕክቷ ይቀጥልና

“ምናልባት ዊሊያምስ ትክክል ከሆነና እሱ በሚገልፀው የአደንዛዥ ዕፅ
ቀለበት ውስጥ ፖሊሶች የሚገኙበት ከሆነ ጆንሰን እዚህ ነገር ውስጥ
እንደሚገኝበት አልጠራጠርም። ለምን ብትለኝ፣ እሱ የቀድሞ የፀረ አደንዛዥ
ዕፅ የፖሊስ ቡድን አባል ነበር፡፡ በዚያ ላይ ሲነየር ነው። ይህ የግድያ ወንጀል ምርመራ እንዲሰጠውም የጠየቀው እራሱ ነው:: የወንጀል ምርመራውንም ሆን ብሎ እያበላሽ እና ውንጀላውንም ወደ እኔ እያቀረበ ምርመራውን እርባና ቢስ እያደረገው ነው።”

እያለ ይቀጥላል። እርግጥ ነው በተለይ ከዊሊያምስ ሞት በኋላ የኒኪ የጭፍን ፍራቻ እና ግምት ቢጨምር አይፈረድባትም:: ስለ ጆንሰን ጉድማን
ምንም ሊያደርግ አይችልም፡፡ ምክንያቱም አብሮት የሚሰራ ባልደረባው ነው።

“ሎው ከጆንሰን ጋር እየሰራህ እስከሆነ ድረስ አደጋ ውስጥ ነህ፤ እና ራስህን ጠብቅ:: እንድትጎዳ አልፈልግም። እኔም ብሆን አደጋ ውስጥ ስላለሁ ላልተወሰነ ጊዜ ከማንኛውም የግንኙነት መስመር ውጪ ነኝ።

ኒኪ ሮበርትስ”

ይላል የላከችለት ኢ ሜይል፡፡

ለምን ያህል ጊዜ ከግንኙነት መስመር ውጪ እንደምትሆን ያለማወቁ
ጉድማንን አሳስቦታል፡፡ ኢ ሜይሏ ከደረሰው እና ካነበበው በኋላ ሁለት ጊዜ
ደውሎላታል፡፡ ኢ ሜይልም ልኮላታል ግን ስልኳ ዝግ ነበር፡፡ ጆንሰን ከመፀዳጃ ቤት ተመልሶ ቦርጫም ሆዱን እያሻሸ “ቡናው ውስጥ ምንድነው የጨመሩበት? መፀዳጃ ቤት ውስጥ እኮ ተቀምጬ ልክ በምጥ ልጅ እየወለድኩኝ ያህል ነበር የተሰማኝ” አለ፡፡
ጉድማንም አፍንጫውን እያራገበ “ምነው በጣም አብራራኸውሳ? አሁን ወደ ፎሬንሲክ መርማሪዎቹ አንሄድም?” አለው፡፡

“አንተ ዝግጁ ከሆንክ ምን ገዶኝ፡፡ መቼስ ፎሬንሲኮቹ አንድ ነገር ሳያገኙ አይቀሩም፡፡ ምክንያቱም ዊሊያምስ ቢያንስ ግማሽ የሎስ አንጀለስ ህዝብ
ጠላቱ ነው። እኔም ልገድለው ትንሽ ነበር የቀረኝ።” አለውና ተነስቶ ሲወጣ
ጉድማንም ተከተለው።

ከሎስ አንጀለስ ሃምሳ ማይል ርቀት ላይ በርሃው ውስጥ የሚገኘው የሲኞራ ማርቼስ የገጠር ሆቴል ቀለል ተደርጎ ነው የተሰራው፡፡ ምንም እንኳን ሆቴሉ በርሃ ላይ ቢሰራም የየክፍሎቹ ኮርኒስ ላይ ካለው ፋን በስተቀር ሌላ ኤየር ኮንዲሽነር አልተገጠመለትም፡፡ ያም ሆኖ የሆቴሉ ነጭ ግድግዳ እና በዙሪያው የተተከሉት የዘንባባ ዛፎች ሁሉንም የእንግዳ ማረፊያ
ክፍሎች ቀዘቅዝ ያደርጓቸዋል።

ኒኪ ወደዚህ የእንግዳ ማረፊያ የመጣችው ዊሊያምስ ከሎስ አንጀለስ ርቃ የማትታወቅበት ቦታ እንድትደበቅ ስለነገራት እና ለማረፍም ጭምር ነው::
የእንግዳ ማረፊያውን ያሳያት ዶውግ ነው። የተጋቡበትን አንደኛ ዓመት
ሲያከብሩ ነው እዚህ ይዟት የመጣው ትዝ ይላታል ቦታው
👍4
ላይ ስላመጣት በኩራት ተሞልቶ እና ወገቧን አቅፏት አይኗን በፍቅር እያየ “ስለዚህ ቦታ
ከሀብታም ጓደኛቹ ስምቶ የነገረኝ ሀዶን ነው። ቦታውን ወደሽዋል አይደል?”

“እጅግ በጣም” ብላው ነጠላ ጫማዋን ክፍሉ ውስጥ ወርውራ እንደ ህፃን
እየቦረቀች ወደ መታጠቢያ ቤት የገባችበትን ሁኔታ አስታወሰችና አሁን ምን ያህል ከዚያን ጊዜዋ ኒኪ እንደተለየች አሰበች። እዚህ ቦታ ለመጨረሻ ጊዜ የመጣችው የዛሬ አምስት ዓመት ከዶውግ ጋር ቢሆንም እሷ ግን በጣም የቆየች ነው የመሰላት።

ትላንትና ማታ ይዛው የነበረውን ሻንጣ ነው ያመጣችው። ሻንጣውን አልጋው ጎን አስቀምጣ አልጋው ላይ አረፍ ካለች በኋላ ስልኳን ስትከፍት የመልዕክት መዓት በሰልፍ ይገባላት ጀመር፡፡ ጉድማን፣ ጉድማን፣ ጉድማን፣ ግሬቸን፣
ግሬቸን... ስልኳን መልሳ አጠፋችው::
ማንንም ማናገር አትፈልግም። የእንግዳ ቤቱ ባለቤት እና አስተዳዳሪ የሆኑት ሲኞራ ማርቼስ በሩን በዝግታ አንኳክተው ወደ ውስጥ ከገቡ በኋላ “ዶክተር ሮበርትስ ለምን ያህል ጊዜ ነው ለመቆየት የፈለግሽው? ያው በፊትም እንደምታውቂው ይህ ክፍል እስከ ሰኔ
ድረስ ክፍት ነው::” አሏት፡፡
ኒኪም እስቲ ዝም ብለው ለጥቂት ቀናት ብለው ይያዙልኝ፡፡ ሀሳቤን ከቀየርኩኝ ደግሞ አሳውቅዎታለሁ።” አለቻቻው እና ተሰናብተዋት ወጡ።

ኒኪ ሲኞራ ማርቼስን ስታናግር ፊቷን የግድ ፈገግ አድርጋ ነበር። ልክ ክፍሉን ለቀው እንደወጡ ግን ወደ ድብርቷ ተመለሰች። ለጥቂት ሰከንዶች
እንኳን ደስተኛ መምሰሏ ህመም ነው የሆነባት። ልቧ በነበረበት ቦታ ላይ
የሆነ በእሳተ ጎመራ ፍም የሆነ፣ ሲነኩት እጅግ የሚያቃጥል እና በንዴት
የሚንቀለቀል የአለት ቅርፊት ያለ ነው የሚመስላት።

ደውግ ሆይ ደስተኛ ለነበርንባቸው ትዝታዎቻችን ሁሉ የተረገምክ ሁን
ዶውግ ሆይ ስለ ውሽትህ፣ በእኔ ላይ ሴት ስለመደረብህም የተረገምክ ሁን! ከዚያች ሩሲያዊት እና ካልተወለደው ልጃችሁ ጋር ለዘላለም በገሃነምእሳትም ተቃጠሉ!

ሊነጋጋ ሲል ኒኪ ለአኔ ቴራፒስቷ ሆና እንደማትቀጠል ነገረቻት “አኔ ሌላ ሰው ጋር የቴራፒ ህክምናውን መውሰድ ይኖርብሻል። አኔ አሁን በጥሩ
ሁኔታ ውስጥ ስላልሆንኩኝ ልረዳሽ አልችልም።” ስትላት አኔ ቅር እያላትም
ቢሆን ተቀብላዋለች፡፡

ማታ ላይ በኒኪ እጅ ላይ ስላየችው ሽጉጥ አኔ ምንም ነገር አልጠየቀቻትም። አዎን ኒኪ ከዚህ በኋላ አኔን እንደ ብረት ልታያት አትችልም:: ኒኪ ውስጥ ያለው ትልቅ የንዴት ሰይጣን እስካልሞተ ድረስም ኒኪ የማንም ረዳት ለመሆን እንደማትችል ገብቷታል። ፀሐይ ከመውጣቷ በፊት ተሰነባብተው ሲለያዩ ሁለቱም ዳግመኛ እንደማይገናኙ እያሰቡ ነበር።

አኔን ከሸኘቻት በኋላ ኒኪ አራት ኢ ሜይሎችን ፃፈች። የመጀመሪያው
ለጉድማን የፃፈችው ደብዳቤ ነው፡፡ ሁለተኛው እና ሦስተኛው ኢ ሜይል
ደግሞ ለካርተር በርክሌይ እና ለላና ግሬይ ሲሆን የቴራፒስት አገልግሎቷን
ማቋረጧን እና ሌላ ቴራፒስት እንዲፈልጉ የሚያሳስብ ደብዳቤ ነው።
አራተኛው ኢ ሜይል ደግሞ ለዕደለ ቢሷ ረዳት ሰራተኛዋ ኪም ቾይ ከስራዋ
እንደተሰናበተች እና የሦስት ወር ደሞዟንም በአካውንቷ እንደላከችላት
የሚገልፅ ደብዳቤ ነበር፡፡

ለልብ ጓደኛዋ ግሬቸን ኢ ሜይሏን ስትፅፍ ግን ልቧን በጣም ከብዷት ነበር። ደብዳቤው የስንብት እንዳይሆንም ፈርታለች:: ትላንትና ሲያወሩ ኒውዮርክ ሄዳ አዲስ ኑሮ እንድትጀምር የመከረቻትን ነገር አስታውሳ ቢሆንልኝ ብላ ተመኘች። ከዚያማ ግሬቸን እና ቤተሰቧ እሷ ጋር መጥተው የምስጋና ቀን እራትን አብረው ይበላሉ፡፡ ኒውዮርክ የሚገኙ ገበያዎችን
አውደ ርዕዮችን እያዩም እንዲዝናኑ ጭምር እየተመኘች ነበር ደብዳቤውን የፃፈችው።

ኢ ሜይሎቿን ከላከች በኋላ ቁርሷን በላች እና የሎስ አንጀለስ መንገዶች
በትራፊክ ከመጨናነቃቸው በፊት ወደ በርሃው ላይ ወደምትገኘው ሀይኬንዳ
መንደር መኪናዋን ማሽከርከር ጀመረች:: በፊት ላይ ወደ በርሃው ስትጓዝ ከፊት ለፊቷ የተዘረጋውን፣ የማያልቀውን ድንጋያማ እና አሸዋማ በርሃን
እያየች መንዳቱ እራሱ ነፃነትን ነበር ይሰጣት የነበረው። አሁን ግን የዚያን
አይነት ስሜት አልሰጣትም፡፡

ጋቢናው ውስጥ ከጎኗ ከሚገኘው ወንበር ላይ ያጠፋችው ስልኳ እና ትላንትና ኪም ቾይ ከቢሮ የኒኪ ቤት ድረስ ይዛላት የመጣችው ዴሪክ ዊሊያምስ የላከላት ደብዳቤ ተቀምጠዋል። ደብዳቤው ወደ ኒኪ ቢሮ የደረሰው ዊሊያምስ ከመሞቱ ከአራት ሰዓት በፊት ነበር፡፡ ኪም ቾይ ፖሊሶች እንደተለመደው መጥተው ብርበራ ከማካሄዳቸው በፊት አስቀድማ ወደ ኒኪ ቤት በመሄድ ነበር የፓስታ ሳጥን ውስጥ ያስቀመጠችላት። ኒኪም ጠዋት
ላይ ሳጥኑን ስትፈትሽ ነበር ደብዳቤውን አግኝታው ይዛው የመጣችው::
ውስጡ ምን እንደተፃፈ እያሰበች መኪናውን ማሽከርከሩ እራሱ ጣር ነው
የሆነባት፡፡

ራሷን አደፋፍራ ደብዳቤውን ለማንበብ ስትዘጋጅ ነበር እንግዲህ ሲኞራ
ማርቼስ ያቋረጠቻት። በድጋሚ ድፍረት ለማግኘት ስላልቻለች ደብዳቤውን
አስቀመጠች:: ፒኪኒ እና የጡት ማስያዢያዋን አድርጋ እና ቀዝቃዛ መጠጥ ከፍሪጅ ውስጥ አውጥታ ስልኳንም ከፍታ እና ይዛው የእንግዳ ማረፊያው ግቢ ውስጥ ወደሚገኘው የዋና ቦታ አመራች። ዋናው አጠገብ ከሚገኘው የማረፊያ አልጋ ላይ ጋደም አለች። የበርሃው ሙቅ ነፋስ ሰውነቷን
እየዳስሰው ሲያልፍ ቀዝቃዛውን መጠጥ ጨለጠችው።

ከምኔው እንደተኛች አልታወቃትም:: ብቻ ፀሀዩ መላ ሰውነቷን አንድዷታል፡፡ አፏም ክው ብሎ ደርቋል፡፡ ቀና ስትል አንዲት ሰፊ የፀሐይ ባርኔጣ ያደረግች ሴት ቁልቁል እያየቻት “ምን ሆነሽ ነው? ለምንድነው
ስልኩን የማታነሺው? እዚህ እኮ ልናርፍ ነው የመጣነው:: ያለበዚያ ደግሞ
ስልኩን ማጥፋት ነው::” ስትላት የሚንጫረረው ስልኳ ተሰማት።

“ሄሎ” አለች ኒኪ፡፡

“ሆ እግዚአብሔር ይመስገን... ብደወል ብደውል እኮ አታነሺም” አለቻት
አኔ፡፡ እና በመቀጠልም “ኒኪ የማወራሽ ነገር አለ በቶሎ መገናኘት አለብን”
“ጠዋት ላይ አውርተን ተለያይተን አይደል እንዴ ይቅርታ አኔ ልረዳሽ አልችልም፡፡” አለቻት ኒኪ፡፡

አኔም እያለቀሰች “የግድ መገናኘት አለብን ስለ ሉዊስ ያወቅኩት አዲስ
ነገር አለ፤ ነገሩ አንቺንም የሚመለከት አደገኛ ነገር ነው::” ስትላት ኒኪ
ምናልባት ዊሊያምስ የነገራት ነገርን አኔ ያወቀች መሰላት።

“ታዲያ ለምንድነው ወደ ፖሊስ የማትሄጂው?” ብላ ኒኪ ጠየቀቻት፡፡

“በፍፁም አይሆንም ፖሊስ ጋ መሄድ የለብኝም:: እባክሽን አንዴ ብቻ
ላግኝሽ፤ ከዚያ በኋላ ሁለተኛ አላስቸግርሽም” ብላ አኔ እያለቀሰች ለመነቻት።

ኒኪም ትላንትና ማታ አኔ የእሷን ህይወት እንዳተረፈችላት ከግምት ውስጥ አስገብታ ልታገኛት ወሰነች::

“እሺ ነገ ማታ 12 ሰዓት ላይ ቢሮዬ ላግኝሽ”
“ቢሮሽ አይሆንም። ሉዊስ በአንቺ ቢሮ፣ በእኔ ቤት፣በ አንቺ ቤት እና
ትራ በኦርኬስትራ ቦታ ጭምር ሰዎች አሉት። ባይሆን የልብስ ማምረቻው ሰፈር
ውስጥ አንድ ባዶ የመጋዘን ህንፃ አለ፤ እዚያ አስራ ሁለት ሰዓት ላይ እንገናኝ::” ብላ አኔ መጋዘኑ የሚገኝበትን ትክክለኛ ቦታ እና የህንፃውን ቁጥር ከእነ በሩ ኮድ ነግራት ስልኩን ዘጋች:: ኒኪም አኔ በዚህ ሁኔታ እጅግ በጣም ተረብሻ አይታት ስለማታውቅ በቀጠሮው ላይ ለመገኘት ወሰነች።......

ይቀጥላል
👍1
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_አርባ_ስምንት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

...ኒኪ ጠዋት ላይ ከእንቅልፏ ስትነቃ ሙሉ በሙሉ የእረፍት ስሜት ነው የተሰማት:: ምናልባትም ከብዙ ቀናት በኋላ ያልተቋረጠ እንቅልፍ ስለተኛች
ሊሆን ይችላል እንደዚህ አይነት ስሜት ሊሰማት የቻለው። ትላንትና የተሰማት ሀዘን እና ንዴትም በእንቅልፍ ወጥቶላታል፡፡ ትላንትና ማታ ሰውነቷን ያስመታችው ፀሐይ አፍንጫዋን እና ትከሻዋን በደንብ አድርጎ ስለጠበሰው ቀይ ሆኗል፡፡ ስለዚህም የሎዕ ጄል ተቀብታ ለጥቂት ጊዜ ያህል ቆየች እና ገላዋን ታጠበች ቁርሷንም እንቁላል ፍርፍር ከተጠበሰ ፍራፍሬ ጋር በልታ በላዩ ላይ ሁለት ኩባያ ጠንካራውን የኢጣሊያን ቡና ጠጣችበት።

ዛሬ ማታ አኔን ማግኘት አትፈራም፡፡ አኔን ካገኘቻት እና ስለ ሉዊስ አገኘሁት ያለችውን መረጃንም ከአኔ ከተቀበለች በኋላ አኔን በደንብ መክራት እንድትረጋጋ ካደረገቻት በኋላ መረጃውን ለሉው አሳልፋ ትሰጣለች፡፡ ከዚያም ነገሮች እስኪረጋጉ ድረስ ወደ ፓልም ስፕሪንግ፣ ወደ አሪዞና ወይንም ደግሞ ወደ ሆታሆ አምርታ ተደብቃ መቆየት ትችላለች፡፡
ወደ እንግዳ መቀበያው አምርታ “ሲኞራ ማርቼስ አሁን ወጥቼ በጣም አምሽቼ ነው የምመለሰው እና ምናልባት የግቢው በር ቁልፍ ያስፈልግ። ይሆን?”

“አያስፈልግሽም ዶክተር በክፍልሽ ቊልፍ የግቢውን በር መክፈት ትቺያለሽ፡፡ ይልቅ እራት ፍሪጅ ውስጥ ላስቀምጥልሽ?”

“ፍራፍሬ ብቻ ይቀመጥልኝ” ብላቸው ወደ መኪና ማቆሚያው ሥፍራ አመራች። መኪናዋንም አስነስታ ከግቢው መውጣቷን የተመለከቱት ሲኞራ
ማርቼስ የስልኩን እጀታ አንስተው የሆነ ቁጥር ላይ ደወሉና “አሁን ከዚህ
ተነስታለች” ብለው ስልኩን ዘጉ።

ኒኪ መኪናዋን እያሽከረከረች ፓልም ስፕሪንግ ደረሰች እና የክፍያ መንገዱ ውስጥ ከመግባቷ በፊት ነዳጅ ለመቅዳት ነዳጅ ማደያ ቆመች:: ወደ ቦርሳዋም እጇን ሰድዳ የገንዝብ ዋሌቷን ልታወጣ ስትል እጇ የዊሊያምስን ኤንቨሎፕ ነካ። ኤንቨሎፕን ቀደደችውና ውስጡ ያለውን ወረቀት አንድ በአንድ አወጣች።

መሪዋ ላዩ ተደፍታ ሰውነቷ የሚርገፈግፈውን ሴት ያየው የነዳጅ
ማደያው አስተናጋጅ ወደ እሷ ቀረበ እና “ችግር አለ የኔ እመቤት?” ብሎ
ጠየቃት፡፡ ኒኪም ቀና ብላ ስታየው በአንድ ጊዜ እያለቀሰች እና እየሳቀች መሆኗን
አየና ትንሽ ቀለል አለው:: በእጇ ላይ የያዘቸውንም ወረቀት እያሳየችው
“ደረሰኝ (ቢል) እኮ ነው አይገርምም?” ብላ ከት ብላ ሳቀች እና “አይገርምም
እሱ ከሞት መንደር የላከልኝ የመጨረሻው መልዕክት የሚያዚያ እና
የግንቦት ወር ክፍያ መጠየቂያ ቢሉን ነው” ብላ ከት ብላ መሳቋን ቀጠለች።

የነዳጅ ማደያው ሰራተኛ ሴትዮዋ ቢሉን እያሳየችው እንደ ዕብድ የሳቀችበት ምክንያት አልገባውም፡፡ እዚህ ፓልም ስፕሪንግ ውስጥ እንደ እሷ ያሉ ዕብዶችን እያስተናገደ በሚያገኘው ዶላር ዕዳውን የሚከፍለው በሚመጡለት ቢሎች ነውና ቢል ይሄንን ያህል ሊያስቅ አይችልም ብሎ በኒኪ ተበሳጨባት፡፡

ጉድማን ቢሮው ቁጭ ብሎ በዴሪክ ዊሊያምስ ላይ የቀረበውን የፎሬንሲክ
ሪፖርት ደግሞ እያነበበ ነው:: ሪፖርቱ እንደሚገልፀው ከሆነ በሟቹ ላይ
ምንም አይነት አሻራም ሆነ የገዳይ ዲ.ኤን.ኤ ሊገኝ አልቻለም:: የተመታበት
ጥይትም ቢሆን አብዛኛው የሎስ አንጀለስ ህብረተሰብ በሚይዘው የሽጉጥ ጥይት ነው:: ነገር ግን ሽጉጡ ላይ የተገጠመው ሳይለንሰር በጣም ልዩ እና በፍፁም ድምፅ እንዳያሰማ የሚጠቅም በመሆኑ፣ እንዲሁም ደግሞ እነዚህን ልዩ ሳይለንሰር የሚሸጡት የጦር መሳሪያ መደብሮች የሚሽጡለትን ሰው አድራሻ እና ማንነት መዝግበው ስለሚሸጡ፣ ይህንን ሊያጣራ ጆንሰን በከተማው ውስጥ የሚገኙ መደብሮች ውስጥ እየዞረ ይገኛል፡፡

ጉድማን የዴሪክን ገዳይ እንደዚህ በቀላሉ እንደማያገኙት እርግጠኛ ነው።
አሁን እያሳሰበው ያለው ነገር የኒኪ ሮበርትስ ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱም እሷ
የገባችበትን አደጋ አታውቅም። የእሷ ከተማውን ለቆ መውጣትን ለጆንሰን
አላሳወቀውም። ይሄ ደግሞ ሌላ ችግር ነው የሚፈጥርበት። ምንም እንኳን እሷ በዊሊያምስ ግድያ ውስጥ ባትሳተፍም የግል መርማሪዋ በተገደለ ማግስት ሎስ አንጀለስን ለቅቃ መጥፋቷ ጥሩ ነገር እንዳልሆነ በደንብ ይገባዋል።

በዚህ ሀሳብ ውስጥ እያለም ላቲሻ ሀል የምትባለው የጣቢያው መልዕክት
አቀባይ አንድ የተከፈተ ኤንቨሎፕ አምጥታ ሰጠችው::ጉድማንም የኢንቬሎፑን መከፈት ተመልክቶ “ኢንቨሎፕን አንቺ ነሽ
እንዴ የከፈትሺው!?” ብሎ በቁጣ ጠየቃት፡፡

“ኧረ በፍፁም” ብላ እሷም ኮስተር ብላ መለሰችለት፡፡

“እና ቅድም ከሁለት ሰዓት በፊት ፖስታ በሚከፋፈልበት ጊዜ ለምን
አልሰጠሺኝም?”

“ምክንያቱም መፀዳጃ ቤት በነበርኩበት ጊዜ ነው የሆነ ሰው መጥቶ ዴስኩ ላይ ያስቀመጠው:: ኤንቨሎፕ ላይም ለሎው ጉድማን የሚል ፅሁፍ ስለተፃፈበትም ነው ላንተ ይዤልህ የመጣሁት” አለችው፡፡
ጉድማን ከኤንቬሎፑ ውስጥ ያለውን ወረቀት ሲያወጣው ዴሪክ ዊሊያምስ ለኒኪ የላከው የሚያዚያ/ግንቦት ወር የክፍያ መጠየቂያ ደረሰኝ እና
ከደረሰኙ ላይ የተቀደደ እና ኒኪ የፃፈችበት ወረቀትን አገኘ። ከደረሰኙ ጀርባ ላይ 777 የሚል ፅሁፍ ተፅፎበታል፡፡ ከደረሰኙ በተቆረጠው ወረቀት ላይ ደግሞ “ይሄን መልዕክት እንደምታገኝው ተስፋ አለኝ፡፡ ነገሩ ከእኔ ይልቅ ለአንተ አስፈላጊ ነው። ሉው
ሁሌም ራስህን ጠብቅ፡ እኔን በፍፁም
እንዳትከተለኝ፡፡ እርግጠኛ ነኝ ጆንሰን እዚህ ነገር ውስጥ እስከ አፍንጫው
ነው የተዘፈቀበት ኒሮ

የሚለውን መልዕክት እንዳነበበወደ መስኮቱ በፍጥነት አመራና ወደታች ወደ ታች ወደ መኪና ማቆሚያው ተመለከተ፡፡
መንገዱ ግራና ቀኝ ላይ።
ከሚራመዱት ሰዎች ውስጥ ኒኪን በአይኑ ቢፈልጋት ሊያገኛት አልቻለም።
ኒኪ ለጥቂት ከእጁ ስላመለጠችውም በጣም ተናደደ፡፡

ወዳ ላቲሻ ዞሮም “ጆንሰን ጋ ደውይለት:”
“ደውዬ ምን ልበለው?” አለችው ላቲሻ ግራ ተጋብታ፡፡

“በአስቸኳይ ወደ ቢሮ እንዲመጣ ንገሪው።” አላት፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ኒኪ ለአኔ የሰጠቻት አድራሻ በሳን ጁሊያን መንገድ ላይ የሚገኝ የድሮ መጋዘን የነበረ ህንፃ ነው። ህንፃው በአንድ ማተሚያ ቤት እና በአንድ የሴቶች ልብስ ስፌት ፋብሪካ መሀከል የሚገኝ ድብቅ ህንፃ ነው::

በእነዚህ ምንም በሌለባቸው ህንፃዎች ውስጥ በፊት ላይ ቤት አልባ
ሰዎች ይኖሩባቸው ነበር፡፡ አሁን ላይ ግን የከተማው ከንቲባ ለቤት አልባ ሰዎች ማደሪያ ስላዘጋጁላቸው አብዛኛዎቹ እዚህ አካባቢ የሚገኙ ህንፃዎች ባዷቸውን ነው የሚያድሩት።

ኒኪ መኪናዋን በቅርብ ርቀት ከሚገኙት ብሎኮች አጠገብ አቁማ ወደ ቀጠረቻት ህንፃ ስታመራ ለአኔ ይበልጥ መጨነቅ ጀመረች። ኒኪ ጭር ባለ ቦታ አኔ ላግኝሽ እና ላውራሽ ማለቷ በተለይ ደግሞ ይሄንን ቦታ መምረጧ ልታካፍላት ያሰበችው ሚስጥር ከፍተኛ ከመሆኑም በላይ አብረውም እንዳይታዩ በመፈለጓ የተነሳ ነው ብላ አሰበች፡፡ “ይሄ የመገናኛ ቦታ ሳይሆን የመደበቂያ ቦታ ነው። ግን ከማን ነው የምትደበቀው?”

የመጀመሪያ ግምቷ ሉዊስ ነው ሊጎዳት ያስበው የሚል ነበር። ግን ከዚህ
ሁሉ ጊዜ በኋላ ለምንድነው ሉዊስ አኔ ላይ ጉዳት የሚያደርሰው? ምናልባት
ሉዊስ ቀናተኛ እና ሁሉንም ነገሮቿን መቆጣጠር የሚወድ ሰው ስለሆነ
ሊሆን ይችላል፡፡ ስለዚህ ሊያስፈራራት እና ተመልሳ ወደ ቤቷ እንድትሄድ
ማድረግ ነው የሚችለው እንጂ አንድም ቀን እጁን አንስቶባት አያውቅም።
ምክንያቱም በጣም ነው የሚወዳት

ትናንት አኔን በስልክ ስታወራት ከድምጿ ውስጥ ከፍተኛ ፍራቻ እና ተስፋ መቁረጥን
👍1
ለመስማት ችላለች፡፡ ስለዚህም አኔን ለአንዴ እና ለመጨረሻ
ጊዜ ከረዳቻት በኋላ ወደ መደበቂያዋ ለመመለስ ወስና ነበር ወደ እዚህ ቦታ
የመጣችው::
የተቃጠሩበት ህንፃ በር ላይ እንደ ደረሰች የእጅ ሰዓቷን ስትመለከት ከቀኑ 11:15 ነበር።አኔ የሰጠቻትን ባለ አምስት ዲጂት ቁጥርን ከግድግዳው ላይ ከሚገኘው ማሽን ላይ ስትጫንም በሩ መከፈት ጀመረ። በሩ ሙሉ በሙሉ እንደተከፈተም ከፊት ለፊቷ ወደ ፎቁ የሚያስወጣ ደረጃን
ተመለከተች። የሚንሸራተተው በር
ነው የተከፈተው፡፡ አኔ እንዳለቻትም “ወደ ውስጥ ከገባሽ በኋላ እኔ እንኳን ብዘገይ ውስጥ ሆነሽ እንደምትጠብቂኝ ቃል ግቢልኝ” ብላት ነበር።

ወደ ውስጥ ከገባች በኋላ ኒኪ የለበሰችውን ልብስ ወደ ራሷ አጥብቃ
በእጁ ያዘችው። ህንፃው ከመቀዝቀዙም በላይ ምንም አይነት መብራት አይታያትም፡፡ ከግድግዳው ላይ በሚገኙት ሁለቱ ቆሻሻ መስኮቶች በኩል
በሚገባው ደብዛዛ ብርሃን ግራጫ የአዳራሹን ወለል በየቦታው የተቀመጡ
የፕላስቲክ ወንበር እና ጠረጴዛዎች እና ወለሉ ላይ ተበታትነው የተቀመጡ
ውዳቂ ቁርጥራጭ ጨርቆች ይታይዋታል። ከጥግ ግድግዳው ላይ ሁለት ትላልቅ በር ያለው አሳንሰር ቆሟል። አሳንሰሩ ትልቅ ነው፡፡ ከአሳንሰሩ ግራ
እና ቀኝ በኩልም ለእሳት አደጋ ጊዜ መውጫ የሚያገለግሉ ሁለት የብረት
ደረጃዎች ወደ ላይ ወደ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ፎቅ የሚያስወጡ ናቸው::

“እኔ” ብላ ኒኪ ስትጠራ አዳራሹ ውስጥ ድምጿ አስተጋባ፡፡ ምንም አይነት መልስ አላገኘችም::

ወደ የእሳት አደጋ መውጫው ደረጃ አመራች። ወደ ላይ መድረክ
የሚመስለው ቦታ ላይ ወጣች። ወደሚቀጥለው ህንፃም በደረጃውም ላይ ወጣች። እዚህኛው ህንፃ ላይ ስትደርስ ደግሞ ረዥም ኮሪደር አጋጠማት። በኮሪደሩ ዳር እና ዳር የተከፋፈሉ ክፍሎች ይገኛሉ። ይህ ህንፃ ከታችኛው ህንፃ ይበልጥ ይጨልማል፡፡ ኮሪደሩ በጣም መጥፎ ሽታ አለው። ሽታው የሰው ሰገራ እንደሆነ ማሽተት ችላለች። ኒኪ ግድግዳው ላይ የሚገኘውን ማብሪያ ማጥፊያ ተጫነችው፡፡ የፍሎረሰንቱ መብራትም መስኮት አልባ በሆነው ክፍል ውስጥ በራ።

እንደ ክርስቶስ ጣውላ ላይ በምስማር ተመትቶ ራቁቱን የተሰቀለ ሬሳ ኒኪ በግማሽ ጉሮሮዋ ተከፍቶ በጣም ደንግጣ ጮኸች። ከፊት ለፊቷ ልክ
ይታያታል። ሬሳው በጣም ከመደብደቡ እና በስለት ከመተልተሉ የተነሳ
የሰውዬው ፊት አይለይም:: ግን ኒኪ በጣም ትኩር ብላ ስትመለከተው
ማንነቱን ለማወቅ ቻለች፡፡ ዊሊ ባደን!

የሆነ ሰው ብዙ ዶላሮችን አፉ ውስጥ ጠቅጥቆበታል። ይሄ ደግሞ በጣም
አሰቃቂ ግድያ እንደተፈፀመበት ያሳያል። ኤክስፐርት ባትሆንም ከሬሳው ላይ
ደም ስለሚንጠባጠብ ዊሊ በቅርቡ እንደሞተ ገመተች።

ኒኪ! እዚህ አለሽ?!” ብላ አኔ ድምጿን አቅጥና ተጣራች::

“አኔ!” ብላ ከባደን ሬሳ ወደ ኋላ ፊቷን ስታዞር አይኗ ላይ ሀይለኛ ብርሃን አረፈበት “የት ነው ያለሺው? ላይሽ አልቻልኩም”

ይሄኔም አንድ ትልቅ ሳጥን ከሚመስለው ቢሮ ውስጥ ወጣች እና በረዥሙ ኮሪደር ላይ ወደ ኒኪ መራመድ ጀመረች፡ የተሰቀለውን ሬሳ በጨረፍታ ካየች በኋላም እየተንገዳገደች ወደ ኒኪ መምጣት ጀመረች። አኔ ኒኪ አጠገብ ስትደርስ ኒኪ በአኔ ፊት ላይ ቧጨሮዎችን ተመለከተች::አይኗ፣ የቀኝ ጉንጫ እና አንገቷ ሰማያዊ ግራጫማ ከመሆናቸውም በላይ አባብጠዋል።

ኒኪም ወደ አኔ ተንደርድራ እየሄደች “መታሽ እንዴ?!”
አኔም በጣም አፍራ የታችኛውን ከንፈሯን ነከሰች።

“ዊሊ ባደንን የገደለው እሱ ነው?” ብላ ኒኪ አኔን አቀፈቻት እና ወደ
ተሰቀለው ሬሳ እንዳታይ እየተከታተለቻት “ሲገድለው እዚህ ነበርሽ? በጣም
አሰቃይቶ እኮ ነው የገደለው”
“ይቅርታ” አለቻት አኔ በጣም እየተንተባተበች። እስከ አሁን ድረስ እጅግ
በጣም ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ነው የምትገኘው።

“ለምንድነው ይቅርታ የምትይኝ?” ብላ ኒኪ በመቀጠልም “ይሄ እኮ ያንቺ
ችግር አይደለም። እዚህ የተደረገው ነገር ሁሉ እኮ አንቺ አይደለሽም ያደረግሽው።”

“ተሳስተሻል” አለች አኔ ሳግ እያነቃት፡፡

“ይሄውልሽ ከዚህ በቶሎ መውጣት አለብን” ብላት ኒኪ በመቀጠል
“እዚህ መቼም ደህንነታችን የሚጠበቅበት ቦታ አይደለም…”

“ጥፋቱ የእኔ ነው” ብላ አኔ አቋረጠቻት እና “በእውነት እኔ ይህንን ባላደርግ... ነገሮች ከዚህ የተለዩ ሊሆኑ ይችሉ ነበር:: ግን እሱ ግድያውን ሲያደርግ እኔ በግድ እንዳየው ነው ያደረገኝ።” አለች እና የባደንን ሬሳ እየተመለከተችም “በቪዲዮ እንድቀርፀው አስገደደኝ ብላ ስልኳን
በሚንቀጠቀጥ እጇ ካሳየቻት በኋላ “አንቺንም ወደ እዚህ እንድጠራሽ
አደረገኝ። በጣም ይቅርታ እሱ ሊያወራሽ ይፈልጋል” አለቻት፡፡

ይሄኔም ከሌላኛው ክፍል ሁለት ግዙፍ ሰዎች ሙሉ ጥቁር ልብሳቸውን
እንደለበሱ ወደ እነርሱ መጡ። እና አጠገባቸው ከደረሱ በኋላም “በዚህ በኩል እንሂድ ሚስዝ ሮድሪጌዝ” ብሎ በትህትና ሲጠይቃት ሌላኛው ወንድ ደግሞ ክንዷን ያዛት። ኒኪም የአኔን ክንድ የያዘው ሰው እጅ ላይ የደረቀ ደም
እየች ሆዷ ተገላበጠባት። ደሙ የሚስኪኑ ዊሊ ባደን እንደሆነ ስላወቀችም
ባደን እዚህ ውስጥ ምን ያደርጋል?” ብላ ራሷን ጠየቀች::

አኔ በሳግ ታፍና እያለቀሰች በሁለቱ ግዙፍ ሰዎች መሀል እየተጎተተች ወደ አሳንስሩ ውስጥ ሲገቡ እያየች ምንም ማድረግ አልቻለችም፡፡

“አንዴ ቆዩኝ!” ብላ ኒኪ እየጠራቻቸው

“እባካችሁ እንዳትጎዷት! እንዳትነኳት!” ብላ ብትናገርም የአሳንሰሩ በር
ተዘጋ።

ኒኪ ሀሳቧን ሰብስባ ለመረጋጋት ሞከረች። ሁለቱን ወንዶች በማየቷ አኔ
ስትበሳጭ እንጂ ስትገረም እንዳላየቻት አሰበች፡፡ ስለዚህም መጥተው
እንደሚወስዷት ታውቅ ነበር ማለት ነው። ምን ነበር ያለቻት “አንቺን እንድጠራሽ አስገድዶኛል ሊያገኝሽ ይፈልጋል ነው አይደል ያለቻት?

ኒኪ ከዚህ ቶሎ መውጣት አለባት። አኔን እንኳን ማትረፍ ባትችል ራሷን ማዳን ይኖርባታል። ወደ ኋላ ተመልሳም በመጣችበት መንገድ ስትመለስ በህይወት እያለ የሊዛ ፍላንገን አፍቃሪ የሆነውን ሰው ሬሳ ትታ በኮሪደሩ ላይ መሮጥ ጀመረች:: ጥቂት ያርድ ያህል ከሄደች በኋላም አንድ ረዥም እና የምታውቀው ሰው ሙሉ ጥቁር ልብሱን እንዳደረገ መንገዱን ዘጋባት::

በጣም ዘና ብሎ ፈገግ ብሎ ቆሞ ሲመለከታት ፎቶውን ዴሪክ ዊሊያምስ
ከጎግል ፎቶ ላይ እንዳሳያት ትዝ አላት፡፡

“ሚስተር ሮድሪጌዝ አለችው፡፡

ሉዊስም ፈገግ ብሎ በቡናማ አይኖቹ እየተመለከታት “ዶክተር ሮበርትስ
በመጨረሻ ላይ በአካል ለመገናኘት በቃን አይደል? ስለመጣሽ ደስ ብሎኛል” አላት

ከኮቱ ውስጥም ሽጉጥ መዝዞ በአይኗ መሀል ላይ ደቀነባት፡፡....

ይቀጥላል
👍2
#የወድያነሽ


#ክፍል_ሰባት


#ድርሰት_ኀይለመለኮት_መዋዕል

...በአቅራቢያችን ያለችው ኮክ ለጋ ቅርንጫፎች ደፋ ቀና እያሉ እርስ በእርሳቸው እየተሳሳሙ ይበተናሉ፡፡ ጉንጯ ላይ ሳም ሳደርጋት የፍቅር ደማቅ ችቦ ተሀኮሰ አፌን ወደጎን አንሸራትቼ የከንፈሮቼን ነዲድ ከከንፎሮቿ አርኪ ገለት ጋር በማጋጠም ምጣድና አክንባሉ ሆንን፡፡ በሕሊናችንም ውስጥ ያ የፍቅር ችቦ ፏ ብሎ ሲቀጣጠል ታየኝ።

የወጣትነት ጣዕም፣ የፍቅር ማራኪ ለዛ፣ አንድ የመሆን ፍላጎት በዝግታ ወደ ውስጣችን ሠረፀ፡፡ ሰማይ እንደ አክንባሎ በላያችን ላይ ተደፍታ ቁልቁል ታስተውለናለች። ምን ግዳችን! የሚንቦገቦጉት ክዋክብት በጨለማው ከርስ ውስጥ የሚገኘውን ነገር ሁሉ ብርሃናዊ ውበት ሊዘሩበት ይታገላሉ። እንደ ገና ለስለስ ብሎ ከሚነፍሰው ነፋስ በተገኘው የቅጠላ ቅጠሎች ውዝዋዜ ላይ የከዋክብት ኅብራዊ ቀዝቃዛ ብርሃን ሲያርፍበት በወርቃማ ቀለም የተለበጠ ዕፅኖታዊ ሥዕል ታየ

እኔ በእርሷ የሕይወት ሰበካ፣ እሷም በእኔ የሕይወት መስክ እየተኩነሰነስን ወደማይታይና ወደማይዳስስ የሰመመን ዓለም ተጓዝን። ጥቂት ደቂቃዎች ዕለፉ፡፡

«እኔ የምልሽ» ብዩ ጀመርኩና «እስኪ ይኸው አሁን ብቻችንን ነን እውነቱን ንገሪኝ ታፈቅሪኛለሽ?» ብዬ ጠየቅኋት። የምትመልስልኝን ለመስማት ጆሮዩን ቀሰርኩ፡፡ አንደበቷን ከባድ ኃፍረት እየተጫነው «የትልቅ ሰው ዘር
ናቸው:: ዞር ብለውም አያዩኝ፣ እኔም የሰው አገር ሰው ነኝ እያልኩ ነው እንጂ
ማፍቀሩንማ መጀመሪያውኑ...» ብላ በዚያ ስስ ጨለማ ውስጥ የፊቴን ሁኔታ
ማየት ትችል ይመስል ትኩር ብላ አየችኝ።

«እንዲሀ አድርገናል፣ እንዲህ ሠርተናል ብለሽ አትናገሪም? ከዚህ ቀደም
በተናገርኩሽና በተቆጣሁሽ ምክንያት አልተቀየምሽም?» ብዬ ሁለቱንም ትከሻዋን ያዝኩ፡፡

«የምን መቀየም? ኸረ እኔ ከየቴ! እንዲያውም ደስ ደስ ነበር የሚለኝ።
እኔ ምክንያታቸውን እንጃ፡ አንድ ሰሞን እናትዎ ፊት ሲነሡኝ ነገሩሩን ሁሉ
ውጩ ዝም ያልኩት እርስዎን በማየት ነበር» ብላ በትኩስ ደም ጢም ያሉ
ጣቶቿን ባንገቴ ዙሪያ ዘረጋቻቸው:: ደቂቃዎቹ ጭልፊት እንዳየች ጫጩት
በነበር ጢሻ ውስጥ ለመሰግሰግ ሸመጠጡ፡፡

«እሜቴና ጌቶች ከተኙ ቆይተዋል» ብሎ በሹሉክታ ገብቶ ምድር ቤት ውስጥ የተኛው ዘበኛ እንዳይሰማን ኮሽታ ሳናሰማ ወደ ውሃው ቧንቧ ተመለስንና ተላያየን፡፡
የውጪውን ደረጃ በቀስታ ከዘለቅሁ በኋላ መብራቱን አብርቼ ወደ ክፍሌ ገባሁ። ወዲያው ልብሴን አወላልቄ አልጋዬ ላይ ተሸመለልኩ፡፡ አምስት ደቂቃ
በማይሞላ ጊዜ ውስጥ የመኝታ ቤቴ በር በዝግታ ተከፈተ፡፡ እሷው መሆኗን
በአረማመዷ ለይቻት ነበር፡፡ ያመጣችውን ውሃ አልጋዩ ሥር ከትራስጌ በኩል
ስታስቀምጥ «ገጭ» የሚል አጭር ወፍራም ድምፅ ሁለት ጊዜ ሰማሁ። በውሃ የረጠቡ እጆቿን በቀሚሷ እያደራረቀች በሩን ቀስ ብላ ከወደ ውስጥ ዘጋችው፡፡ብርድ ልብሱን ከወደ ትከሻዩ በኩል ገልጣ እጅዋን ወደ ውስጥ አሾለከች።ደረቴን አንገቴን ግንባሬንና ጉንጩን ደባበሰችኝ፡፡ እጅዋ ከግንባሬ ላይ እንደተለጠፈ ከተዘጋው የመኝታ ቤቴ መዝጊያ ውጪ ትንሽ ራቅ ብሎ የሚከፈት
በር ሲንሲያጠጥ በመስማቴ ሰውነቴ በጥርጣሬ ተንዘፈዘፈ፡፡ ልቤ በድንጋጤ
የተሰነጣጠቀች መሰለኝ፡፡

የሰው ኮቴ ተሰማ፡፡ ቁልቁል ወደ አልጋው ሥር ለመስረግ ፈለግሁ። የማይሆን አይሆንምና አልቻልኩም፡፡ የኮቴው ድምፅ እየቀረበና እየጎላ መጣ ቀረበ መጣ ቀረበ በሁኔታው ቁጥጥር ሥር በመዋሌ ፈጣን ውሳኔ ለመስጠት አዳገተኝ፡፡ የወዲያነሽ እጅዋን በፍጥነት ከግንባሬ ላይ አነሳችው::ፊቴን ገለጥ አድርጌ ሳይ ከመዝጊያው በስተጀርባ ተለጥፋለች፡፡

በሩ ከወደ ውጪ ተንኳኩቶ መጨበጫው ተነቃነቀ እና ወደ ውስጥ ተገፋ። የወዲያነሽ ከበሩ ላይ ተለጥፋ አብራ እየተገፋች የኋሊት ሄደች፡፡
ረዢም የውስጥ ልብስና ወፍራም ጋቢ ደርባ ራሷን ከፈት ባለው መዝጊያ
በኩል ወደ ውስጥ በማስገባት «ተኝተሃል እንዴ? ምነው ድምዕህ ጠፋ? ደኅና
አይደለህም እንዴ?» ያለችኝ እናቴ ነበረች። ጉድ ፈላብኝ!!

ድንጋጤ ባፈናት ደቃቃ ድምፅ ምላሴ አፌ ውስጥ እየተርበተበተች
«ደኅህ ነኝ፡ ምንም አልሆንኩም። ገና በጊዜ እኮ ነው የተኛሁት። ሂጂ ግቢ ብርድ አይምታሽ» አልኳት የሞት ሞቴን።
የወዲያነሽን ካጋጠማት የጉድ ፍላት ሥቃይና የድንጋጤ ረግረግ ውስጥ
ባስቸኳይ ለማውጣት ስል እናቴ እዚያው እንደቆመች ተሸፋፈንኩ፡፡ ሰውነቴ
ተንቀጠቀጠ። እናቴ ፊት እንደነሡት ቀላዋጭ በሩን ዘግታው ተመለሰች።

የወዲያነሽ በድንጋጤ ድርቅ ብላ ብቻዋን እንደ ቀረች ያጥር ዕንጨት ቆማለች። እጆቿ ደረቷ ላይ ተለጥፈዋል፡፡ እናቴ የመኝታ ክፍሏን በር ስትዘጋና
ትልቅ እፎይታና ግልግል! የወዲያነሽ ከወጥመድ እንዳመለጠች እይጥ በሩን ከፍታ እግሬ አውጭኝ አለች። በላዩ ላይ የወረደው የድንጋጤ ዶፍና ውርጃብኝ ወዲያው ጎደለ። በምትኩም ትዝታ እና ሰመመን እንደገና ደግሞ ትኩስ የፍቅር ሐሳብ አእምሮዬ ውስጥ “ዳንኪራና ሆታ ጀመረ::የወዲያነሽ ፈገግታ ለዛና ግልፅነት ሲነካካኝ ታወቀኝ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
...አባቴ የታላቅ ወንድሙን ጭምትነትና ልበኛነት እያስታወሰ በሚያወራበት ጊዜ ሁሉ ትዝታው በሐሳብ ፈረስ አፈናጣው ወደ አለፉት ዓመታት የኋሊት ትሰግርና ትካዜ መቀመቅ ውስጥ አገርግራ ትጥለዋለች:: መጋቢት አቦን በያመቱ እንደሚዘከርና በታላቅ መንፈሳዊ እምነት
እንደሚያምናቸው ሲያብራራ ፊቱ በኅዘን ተኮፋትሮ ዐይኖቹ በቁጣ ይጎለጎላሉ።

«ወንድሜን የገደለው የገዛ አራሹ ነው። ያውም የዋንጫውን ልቅላቂ ጠጥቶ የገበታውን ፍርፋሪ በልቶ ያደገ፡፡ የወንድሜን ገዳይ ለማስያዝና ከሕግ ፊት
አቅርቤ ለማስቀጣት በተጉላላሁ ጊዜ የደረሰብኝን ከባድ ስቃይ እስከ ዕለተ
ሞቴም አልረሳው:: ታዲያ ስፈልግና ሳስፈልግ ኖሬ ወሎ ውስጥ ከደሴ የትናየት ተንታ ከምትባል ትንሽ ከተማ ውስጥ መኖሩ በጭምጭምታ ታወቀ። ስገሠግሥ ሄድኩ፡፡ እዚያች ከተማ የገባሁት መጋቢት አራት ነበር። በማግሥቱ አሮጌ ሽማዩን ተከናንቤ ስፈልግና ሳስፈልግ ዋልኩ፡፡ መሸታ ቤቶቹ በቁጥር ናቸው።የሰው ደም አይለቅ አይደል! አንዷ ኮማሪት ቤት ተወዝፎ አምቡላውን ሲግፍ አገኘሁት፡፡ ወዲያው በነጭ ለባሽ አስያዝኩና እያካለብኩ ደሴ አስመጣሁት፡፡ገድሎ ዱር መግባቱ ቀድሞውኑ ተመስክሮና ተረጋግጦ አልቆ ስለ ነበር የኋላ ኋላ በስቅላት ተቀጣ፡፡

ልክ ባመቱ ደግሞ የአቦ ዕለት የአጥቢያ ዳኛ ሆኜ ተሾምኩ፡፡ ከአንድ ዓመት በኋላ ደግሞ ልክ የአቦ ዕለት ተካበች፣ ሙሉነህን ተገላገለች። ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሁልጊዜ እንደ ተራዱኝ ነው:: ከዚያ ወዲህ እንደ አቅሜ ጠበል ጠዲቃቸውን አስታጉዬ አላውቅም። አሁንም ቢሆን ሁልጊዜ ከጐኔ እንደ ቆሙ ናቸው፡፡ በጠበላቸውና በቃል ኪዳናቸው ነው ነፍሴ ቆማ የምትሔደው፡፡ እንደ
ሐኪሞቹ በሩን መቀባጠርማ ይኸነዬ እጓሯቸው ነበርኩ፡፡ አሁንም በሆነ
ባልሆነውና በትልቅ በትንሹ በተበሳጨሁ ቁጥር የደም ብዛቴን የሚያስታግሣልኝ
እሳቸው ናቸው። በሳቸው ጠበል ተነክሬ ከእምነታቸው ስቀምስ ዐይኔ ሁሉ
ያበራል» በማለት ያስረዳል።

በያመቱ መጋቢት አምስት ቀን በቤታችን ውስጥ ቅልጥ ያለ ድግስ ይደገሳል፡፡ የሚጠመቀው ጠላ የሚጣለው ጠጅ የሚሠራው ወጥና የሚጋገረው
እንጀራ መጠንና ብዛቱ ምን ያህል እንደሆነ የሚያውቁት እናቴና በየዓመቱ
ለዚሁ ጉዳይ የሚመጡት ሠራተኛ ሴቶች ብቻ ናቸው።

በግቢው ውስጥ ባለው ሰፊ ገላጣ ቦታ ላይ ባንድ ጊዜ ከሁለት መቶ ሰዎች በላይ ለመያዝ የሚችል ድንኳን ይጣላል፡፡ አባቴን ፍርድ ቤቱ የሚያውቀውና ዝናውን የሰማ ዘመድ
👍3
ይሁን እየተግተለተለ ይመጣል፡፡

ከአገር ቤት ካመጡት ሰዎች መካከል አንዳንዶቹ ሦስትና አራት ቀን
አድሪውና ሰንበትበት ብለው አተላ አፋሰው ይሔዳሉ:: ከዋዜማው ጀምሮ
ከደኅነኛው ይልቅ ሰካራሙ ስለሚበዛ ምድረ ግቢው ድብልቅልቁ ይወጣል ፡ የዕለቱ ዕለት ማታ የከተማው ሰው ጥርግ ብሎ ሲሔድ የገጠሮቹ ምድር ቤትና ድንኳን ውስጥ ሲያድሩ ቀሪዎቹ ደግሞ በያታክልቱ ስር ይለሽልሻሉ ጠምብዞ የትም የሚወድቀው ደግሞ ብዙ ነው።

የዓመቱ አቦ አሁንም ጊዜውን ቆጥሮ ደረሰ። ማንኛውም ነገር በቀድሞው
ሁኔታ ተዘጋጀ፡፡ ዕድምተኛውና ቤተኛ ነኝ ባዩ ሁሉ ከያለበት ተሰበሰበ፡፡

የወዲያነሽ በልኳ ያሰፋቸውን የሚያምር ቀሚስ ለብሳና እኅቴ ላንድ ቀን
ያዋስቻትን ሹራብ ደርባ እርጀት ያለ ውራጅ ጫማ አድርጋ በተጋባዦች መኻል
መለስ ቀሰስ ስትል ያዩዋት ሁሉ አይናቸውን ጣሉባት፡፡ ከአሥራ ሁለት ሰዓት በኋላ ተጋባዡና ጠባል ቀማሹ እየቀለለ በመሔዱ ቀሪዎቹና ቤተኛው ሁሉ በድንኳኑ ውስጥ በተንተን ብሎ እርስ በእርሱ መገባበዝ ቀጠለ:: ቀስ በቀስ
አብዛኛዎቸ ሞቅ እላቸው::

እባቴ በበኩላ የፍርድ ቤቶችና በየሙግቱ ምክንያት የሚያውቃቸውን ብዙ ሰዎች ጠርቶ ስለ ነበር ብሉልኝ ጠጡልኝ እያለ ሲጋብዝና ሲሯሯጥ በመዋሉ፣

እናቴም በፊናዋ የግል እንግዶችዋንና እንዲሁም ሌላዉን ሁሉ ወዲያ ወዲህ ስትባዝን በመዋሏ የማታ ማታ ሁለቱን በድካም ዝለው ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ላይ ተኙ፡፡ የውብነሽም ከግማሽ ሰዓት በኋላ
ተከተለች::

ቀደም ሲል ከሶስት ወራት በፊት እናቴ ለወጂያነሽ ታዛዥነትና መልካም ጠባይ ተደስታ ለበዙ ጊዜ ምድር ቤት ውስጥ ተገትሮ የኖረ አንድ አሮጌ የብረት አልጋ ሰጥታት ነበር። እኔም ይህንን ስጦታ አስታክኬ አሮጌ ፍራሼን ጨመርኩላት፡፡

የአቦ ዕለት ማታ ግን ከገጠር የመጡ ጭሰኛ ሽማግሌ በየወዲያነሽ አልጋ
ላይ እንዲተኙ ተደረገ፡፡ አባቴ ስለ እርሳቸው ሲናገር «ታማኝ ሰው ናቸው፡
ምርት ሲሠፍሩ እፍኝ የሰው ገንዘብ አይፈልጉም፡፡ ቀኝ እጅ ናቸው» ይላል፡፡

የወዲያነሽ በድካም የዛለ ሰውነቷን የምታሳርፍበት ምቹ ጥግ አጣች።
የእኔን ልዩ እርዳታ ለማግኘት ዐይኖቿ በዐይኔ ዙሪያ ተንከራተቱ። አፍ አውጥታ
ለመናገር ኃፍረት ስለ ተጫናት ግድግዳውን ተደግፋ መቆም አበዛች።

በእንግዳ መቀበያው ክፍልና በአካባቢው ሰው አለመኖሩ እንደአረጋገጥኩ በቅድሚያ የመኝታ ቤቴን መብራት አጠፋሁ እና ዕቃ ቤቱ በር አጠገብ አንገቷን ሰበር አድርጋ የቆመችውን የወዲያነሽ ነይ አሁን ለጊዜው እዚያ ተኚ» ብዬ በክንዷ ስቢያት ገባሁ፡፡ በሩን በሚገባ ከዘጋሁት በኋላ መብራቱን አበራሁት።

«አይዞሽ አትፍሪ! እዚህ እኔ አልጋ ላይ ወጥተሽ ተኚ፡ ስንገባ ማንም አላየ» ብዬ እየተርበተበትኩ በሩን ዘግቼባት ውልቅ አልኩ፡፡

💫ይቀጥላል💫
👍1
#ፖለቲካ

ምን አስጨነቀህ ----ባታነብ
ባትመራመር -----ባትበቃ፣
ምን ችግር አለው----- ባትበስል
ባትሰለጥን ባትነቃ፡፡
አዳማጭ ባይኖር---- ምንተዳህ
መሰሎችህን አትጣ፣
አጥብቆ ጠያቂ እንዳይገጥምህ
ዙሪያህን እጠር በጋሬጣ፡፡
ክፉ ክፉውን ተናገር
በጎ በጎውን አትንካ፣
ያንተን ጭንቅላት የሚመጥን
ቀላል ስራ ነው ፖለቲካ፡፡

🔘ሻለቃ ወይን ሐረግ በቀለ🔘
👍1
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

....ከኮቱ ውስጥም ሽጉጥ መዝዞ በአይኗ መሀል ላይ ደቀነባት።

...ሚክ ጆንሰን ፖሊሷ ላቲሻ ሆልን ልክ እንደ ቆሻሻ እየተመለከታት

“ጉድማን በቶሎ ይፈልግሃል ብለሺኝ ነበር የመጣሁት” አላት፡፡

“አዎን መርማሪ ፖሊስ ጉድማን እንደዚያ ብለሽ ነው ደውይለት ያለኝ ጌታዬ” ብላ መለሰችለት።

ላቲሻ ከጉድማን ይልቅ ጆንሰን በጣም ንዴተኛ እንደሆነ ስለምታውቅ በጣም
ተጠንቅቃ በትህትና ነበር መልስ የምትሰጠው።ሁሉምዐየዲፓርትመንቱ ሰራተኞች ከሚክ ጆንሰን ጋር ፊት ለፊት መጋፈጥ እንደሚያዋርድ ያውቃሉ። በተለይ ደግሞ የሚጋፈጠው ሰው አይሪሽ ካቶሊክ ነጭ እና ወንድ ከሆነ ጉዱ ነው የሚፈላው፡፡

“እና የታለ እሱ?” ብሎ ጆንሰን ጥርሱን ነክሶ ጠየቃት፡፡

“አላውቅም ጌታዬ!”

“አታውቂም?!” ብሎ ጆንሰን በሹፈት መልክ ድምፁን ቀንሶ ጠየቃት::ክፍሉ ውስጥ ከሚገኘው ሶፋ ወንበር ላይም ሰምጦ ከተቀመጠ በኋላ አይኑን
በመጨፈን ንዴቱን ተቆጣጠረ። ለእሷ አስቦ ሳይሆን ሀይሉን መቆጠብ
ስላለበት ነው ንዴቱን ያላሳያት። አሁን ነገሮች በጣም አደገኛ ሆነዋል።
ስለዚህ አሁን ማወቅ ያለበት ጉድማን የት እንደሚገኝ ብቻ ነው።

ሁለቱ መርማሪ ፖሊሶች እየተወሻሹ እስከ አሁን ድረስ ዘልቀዋል። ዛሬ ላይ ደግሞ ጆንሰን የሽጉጥ ድምፅ አፋኝ የሚሸጡ ሰዎችን ሲያፈላልግ እንዳልዋለ ሁሉ ጉድማንም የመተግበሪያ አፕሊኬሽን ፈቃዱ የማን እንደሆነ ሲመረምር እንደዋለ ያውቃል። ጆንሰን የካርተር በርክሌን ባንክ ወደ ሆነው በርክሌይ ሀሞንድ ሩድ ባንክ ሄዶ ለምርመራ የሚፈልገውን ፋይል ኮፒ ሲያስደርግ በነበረበት ጊዜ ነበር በአስቸኳይ እንደሚፈለግ ይህቺ ደነዝ ሴት
ደውላ የነገረችው፡፡

ዛሬ በርክሌይ ቢሮ ውስጥ ሆኖ ነበር ጉድማን እየዋሸው ሁለቱንም ባሳወራቸው የማይገባው ዓለም ውስጥ አብሮት እንደሚሰራ የገባው። እርግጥ
ነው ገና ይሄንን ጉዳይ አብረው ምርመራ ማድረግ ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ
ደመ ነፍሱ ጉድማንን እንደማያምነው ሲነግረው ነበር።

“መርማሪ ፖሊስ ጉድማን እዚህ አንተን እየጠበቀ ባለበት ጊዜ ላይ ነበር
ስልክ የተደወለለት::” አለች እና ላቲሻ በመቀጠልም “የደወለለትን ሰው ማንነት ባላውቅም ስልኩን ካወራ በኋላ ልክ ከሲኦል ተመንጥቆ እንደወጣ የሌሊት ወፍ በፍጥነት ነበር ከዚህ ቢሮ የወጣው። ፊቱ ላይ የሚታየው ነገርን ሳልጨምር ማለት ነው”

የጆንስን አዕምሮ የተለያዩ ነገሮችን እያሰበ ሆዱን ፍርሃት ፍርሀት አለው።

ላቲሻን ከእሱ እና ጉድማን የጋራ ቢሮ አስወጣት እና በሩን ዘግቶ የጉድማን ወንበር ላይ ቁጭ አለ።

አሁን ነገሩ እየከረረ ነው ፤ ነገር ግን ተስፋ መቁረጥ አይኖርበትም፡፡

አስብ!”

የጉድማን ዴስክ ሁሌም ጥርት ያለ እና የተደራጀ ነው። የዶክተር ሮበርትስ አድራሻ ከጀርባው የተፃፈበት ኤንቨሎፕ እና የጉድማን ስልክ ዴስኩ ላይ ይገኛሉ። ይሄ ደግሞ ጉድማን በጣም በከፍተኛ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ በመሆኑ የተነሳ ነው እንጂ ጉድማን ስልኩን ረስቶ መቼም እንደማይሄድ ያውቀዋል። ጆንሰን ኤንቨሎፕን አንስቶ የዊሊያምስን ደረሰኝ እና ከጀርባው የተፃፈውን የኒኪን እጅ ፅሁፍ ማስታወሻውን በጥንቃቄ ሲመለከት ቆየ።
በተለይ ደግሞ የእሱን ስም ከኤንቨሎፕ ላይ ሲያነብ ልቡን አፈነው። ጆንሰን
እዚህ ነገር ውስጥ እስከ አንገቱ ነው ያለበት! የማትረባ ሴት! አንገት ድረስ
መጥለቅ ምን ማለት እንደሆነ ሊያሳያት ነበር።

ኤንቨሎፕን ኪሱ ውስጥ ከተተ እና የጉድማንን ስልክ አንስቶ ከበፊት
ጀምሮ ሸምድዶ የያዘውን የስልኩን ኮድ ቁጥር ፃፈ እና ከፈተው።የመልዕክት ሳጥኑን እና የደወላቸውን ቁጥሮች በጣቱ ወደ ታች ሲያደርግ ቆይቶ በመጨረሻ ላይ የሚፈልገውን ነገር አገኘ።

ወደ ራሱ ስልክም ከጉድማን ስልክ ላይ ያለውን መረጃ አዘዋወረ እና የተላከ መልዕክት የሚለው ቦታ ላይ ገብቶም መረጃውን አጠፋ:: ሰዓቱን ሲመለከትም ልቡ በፍርሃት መደለቅ ጀመረች፡፡ 12:20 ይላል! ይሄ እንዴት ሊሆን ቻለ? ምናልባት ዘግይቶ ቢሆንስ?

ሽጉጡን እና ተጨማሪ የሽጉጡ ካርታዎች ቀልሃቸው ሙሉ መሆኑን አረጋግጦም በሩን ከፍቶ እየሮጠ ወጣ፡፡

አሁን ይህንን የተረገመ ምርመራ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ መጨረስ ይኖርበታል።

ኒኪ አይኗን ጨፍና ህይወቷን የሚያሳጣትን ጥይት ድምፅ እየጠበቀች
ነው። የዊሊን ሬሳ ስታይ የተሰማት ከፍተኛ ፍርሃት በንኖ ጠፋ እና በተስፋ መቁረጥ ተተካ፡፡ በተለይ ደግሞ ለማወቅ የምትፈልጋቸውን ነገሮች ሳታውቅ
መሞቷን ስታስብ ድንዛዜ ተቆጣጠራት፡፡

የምትጠብቀው የጥይት ድምፅን መስማት አልቻለችም። አይኗን
ስትገልፅም የሮድሪጌዝ አይኖች ላይ ጭካኔን እና መገረምን ተመለከተች፡፡

“ምን ያስቸኩልሻል ዶክተር ሮበርትስ፡፡ ወደ ፈጣሪሽ ከመሄድሽ በፊት ማውራት አትፈልጊም እንዴ?” አላት፡፡

“ዊሊ ባደንን አንተ ነህ የገደልከው?” ብላ በእርጋታ ጠየቀችው። እርግጥ ነው ሊገድላት ነው። ግን ከመሞቷ በፊት መልሶችን መስማት ትፈልጋላች፡፡

“ታዲያስ?” ብሎ ምስጋና የሚሰጣት ይመስል አጎነበሰ፡፡

“ለምን?

“ለምን አልገድለውም?” ብሎ ሳቀባት እና “እንዴ ያደረግኩትን ሥራ እንዳልወደድሽው እያየሁ እንዳይሆን ብቻ! የሆነ አጭበርባሪ አሳማ ነገር እኮ
ነው።”

“ለምን?”

“ተስገበገበአ!” አላት እና በመቀጠልም “አብረን በምንሰራው ቢዝነስ ውስጥ
ሜክሲኮ ውስጥ ከተስማማነው ውጪ ብዙ ገንዘብ ከእኔ ላይ መውሰድ
ጀመረ። ሜክሲኮ እያለን ጠንቃቃ ነበር፡፡ እዚህ ሎስ አንጀለስ ከመጣ በኋላ
ግን ራሱን አይነኬ አድርጎ መቁጠር ጀመረ፡፡” አላት እና ወደ ዊሊ ሬሳ ዞሮ
“ይህ ሀሳቡ ደግሞ የማይረባ እና ስህተት እንደሆነ ላሳየው ፈለግኩኝ። ማንም ሰው ከእኔ ጋር ጠላትነት ውስጥ ከገባ የትም ቢገባ ፈልጌ አገኘዋለሁ::” ካላት በኋላ በጣም በሚያስፈራ ሁኔታ አፍጥጦ ሲያያት ኒኪ ወዲያውኑ ተኩሶ የሚገድላት መስላት:: “እሺ ሌላ ጥያቄ አለሽ?” አላት፡፡

“እኔን ምንድነው ያደረግካት?”

ሮድሪጌዝም በጥያቄዋ ተገርሞ አያት እና
“እኔን እሷ እንዲደረግባት ከምትፈልጋቸው ነገሮች ውጪ ምንም ነገር አላደረኳትም” አለ እና ፈገግ ብሎም
“ሚስቴ ሰዎች እንዲጫኗት ትፈልጋለች። ዶክተር ሮበርትስ አንቺ ይሄ የሚስቴ ነገር ለምን እንዳልገባሽ አላውቅም። አሁንም ቢሆን ይሄ ነገር አይገባሽም። ምክንያቱም አኔን ከእኔ በላይ አታውቂያትም።”

“በጣም እንደምትፈራህ አውቃለሁ” አለችው እና ኒኪ በመቀጠልም
አንተ ሸሽታ ወደ እዚህ የመጣችው አንተ አስረሃት የምትኖረው ኑሮ ከአቅሟ በላይ ስለሆነባት ነው” ስትለው ፈገግታው ጨለመ::

አንቺ ስለ እሷ ስትከራከሪላት ሳይ በጣም ይገርመኛል፡፡ እንዴ! ወደዚህ
ልታስገድልሽ እንደሆነ እያወቅሽ መሆኑ ደግሞ የባሰ አስደምሞኛል።” አላት፡፡

“ምክንያቱም ስላስገደድካት ነው! የዊሊ ባድንን ግድያ አስገድደህ እንድታየው እንዳደረካት ሁሉ ማለት ነው።” አለችው፡፡
ሊዊስም ራሱን በአሉታ ነቅንቆ “ዶክተር ሮበርትስ ነገሩ እስካሁን አልገባሽም ማለት ነው? እሷ ይህንን ነገር የምታደርግልኝ እኮ በጣም
ስለምትወደኝ ነው። ላንቺ ምንም አይነት ስሜት ቢኖራትም በመጨረሻ ላይ
አኔ እኔን ለመከላከል ስትል ማንኛውንም ነገር ታደርግልኛለች። ምንም እንኳን በመካከላችን ያለውን ፍቅር ልታጠፊ ያላደረግሽው ነገር ባይኖርም
አኔ ልቧ አሁንም ከእኔ ጋር ነው።”

“ውሸት!” ብላ ኒኪ ከመለሰችለት በኋላ ግን ደውላ ወደዚህ እንዳስመጣቻትና እንዲሁም ደግሞ በዊሊ ባደን ግድያ ላይ ስለነበራት ድርሻ ምን ይሆን? ብላ
1👍1