#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
...ከሩቅ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ በርሜሎች ሲመለከት ክንዷን ይዞ ወደዚያው ጎተታት፡፡አካባቢውን ባለበሰው የቆሻሻ ክምር ላይ ተሻግረሁ ከበርሜሎቹ ጀርባ ዞረው ሸብረክ ሸብረክ አሉ፡፡በስተግሪ ራቅ ብሎ መደዳውን ከተኮለኮሉት የመሸታ ቤቶች የሚወጣው ደብዛዛ ብርሃን አካባቢውን በድቅድቁ ጨለማ ከመዋጥ አድኖታል ወዲያ ማዶ አንድ የጭነት መኪና ቆሟል፡፡ በስተቀኝ የውሾች ጥል በጨለማ ውስጥ አስተጋባ፡፡ድምፃቸውን አጥፍተው ተጠባበቁ፡፡
ናትናኤል ቀና ሲል በጨለማው ውስጥ አንድ ነገር ውልብ ሲል ተመለከተ፡፡ ዓይኖቹን በሰፊው ከፍቶ በጨለማው ላይ አፈጠጠ፡፡ ድምፅ ተሰማው... እየቀረበች ስትመጣ ሲለያት በእፎይታ ትንፋሽን ለቀቀ።ሰካራም ሴት ነበረች:: እንደመንገዳገድ ትልና ወደፊት ትራመዳለች፡፡ ትንሽ ታንጎራጉርና ደግሞ ወደፊት ተራመዳለች፡፡ ብዙም ሳይቆይ ከሰካራሟ ጀርባ የሌሎች ሰዎች ሩጫ ተሰማ፡፡ ናትናኤል ከበርሜሎቹ ጀርባ ሳይወጣ ጭንቅላቱን ብቻ አቅንቶ ተመለከተ::
ሦስት ሰዎች እየተሯሯጡ በኮረኮንቹ መንገድ መጡ፡፡ በኮረኮንቾ
መንገድ ላይ እየተወለካከፉ ሲሮጡ ናትናኤል አዳኞቹ እንደሆኑ ገባው::
ሰካራሟ ሴትጋ እንደደረሱ ከሦስቱ አንደኛው የያዘውን ባትሪ መለስ አድርጎ
ፊቷ ላይ ቦግ እደረገባት፡፡
“ትዝታ እ.. እባላለሁ፡፡” አለች ሰካራሟ ኣይኖቿን ባትሪው ብርሃን በክንዷ ከልላ “ሀ! ሀ! ሀ! ከፈለግህ ደሞ እቤት እንሂድና::ባትሪውን ያበራባት ሰው ትቷት ከጓደኞቹ ጋር ወደፊት ቀጠለ።
ሦስቱ ሰዎች ወደ ቆሻሻ ማጠራቀሚያዎቹ ሲደርሱ ትንሽ ሲቀራቸው ቆም አሉና ተነጋገሩ፡፡ ወዲያው ሁለቱ በስተቀኝ ታጥፈው በጨለማው ውስጥ ሲሰወሩ ባትሪ የያዘው ሰው በበርሜሎቹ ኣቅጣጫ አመራ፡፡
ናትናኤል አብራው የተደበቀችውን የካልቨርትን ወዳጅ ጠረጠራት፡፡
ብትጮህስ? ብትጣራና ብታሲዘውስ? እዚሁ ቆሻሻ መጣያ በርሜል : ስር
ደፍተውት ሊሄዱ አይደል? ፈጠን ብሎ ቀኝ እጁን በትከሻዋ አሳልፎ አፏን
አፈናትና በግራ እጁ የያዘውን የቢላ ጫፍ አንገቷ ስር ሽጎጠው፡፡
“ትንፍሽ እንዳትይ… ፊቱን ከማዞሩ በፊት ይሄ ቢላ ማጅራትሽ ነው የሚደርሰው፡፡” አላት ዓይኖቹን በበርሜሎቹ አቅጣጫ ቀሮጠው ሰው ላይ ተክሎ፡፡
ሳትነቃነቅ አይኖቿን ብቻ ኣቅንታ በጭንቀት ተመለከተችው::እንገቷ ስር የተሸጎጠው የቢላ : ስሎት ለስላሳ ቆዳዋን እንደ ምላጭ ሲሰነጥቀው ተሰማት::
ሰውየው ወደ በርሜሎቹ እየተጠጋ በመጣ ቁጥር በደመነፍስ ያወቀና የተረዳ ይመስል ፍጥነቱን ቀንሶ የባትሪውን ብርሃን እንደ ነብር ጅራት ከወዲያ ወዲህ እያላጋ ዙሪያውን እየፈትሽ በዝግታ ይራመድ ጀመር፡፡ እየቀረባቸው ሲመጣ ናትናኤል በበርሜሎቹ አናት ላይ ተመለከተው።በግራው ባትሪውን እንደጨበጠ በስተቀኝ የኮት ኪሱ ውስጥ የጨመረውን እጁን ሲመለከት ስውየው መሣሪያ እንደያዘ ናትናኤል ተረዳ፡፡ በየምሥራች አፍ ላይ የጫነውን የቀኝ እጁን ጠበቅ አደረገና በግራው የያዘውን ቢላ ከአንገቷ ስር አውጥቶ ይዞ ተዘጋጀ፡፡ ተጠባበቀ፡፡ ከበርሜሎቹ ዙሪያ
የፈሰሰው ቆሻሻ ላይ ሲረግጥ የአዳኙ ኮቴ ኮሽታ ተሰማው። ሲጠጋውና
ሲቀርበው ሲደርስበት ተወርውሮ ቢላውን ሊሰካበት ተዘጋጀ፡፡ ሰውየው
ድንገት ቆም አለ፡፡ ያመነታ መስለ ባትሪውን ዞር አድርጎ በበርሜሎቹ ላይ
እበራ፡፡ የባትሪውን ብርሃን በዙሪያው አወናጨፈው፡፡ ወዲያው ፊቱን መልሶ
በኮረኮንቹ መንገድ ወደፊት ቀጠለ፡፡
ሰውየው ከራቀ ወዲያ ነበር ናትናኤል ለመተንፈስ የደፈረው።የምሥራችን አፍ ለቀቀና ቀና አደረጋት፡፡
“አይዞሽ አትፍሪ፤ ልጎዳሽ አልፈልግም:: እመኚኝ፡፡ ከዚህ በላይ ምን ማረጋገጫ ነው የምትፈልጊው?” አለ ትከሻዋን በሁለት እጆቹ ይዞ እየነቀነቀ፡፡ “በይ ተነሺ… ሳንቻኮል በእርጋታ እየተራመድን ወደ ዋናው መንገድ እንውጣለን፡፡ ለመሮጥ ወይ ለመጮህ ብትሞክሪ ግን ምርጫ አይኖረኝም::”
“አልሮጥም::” አለች ፊቷን መልሳ በፍርሃት እየተመለከተችው::
ናትናኤል የምሥራችን ክንድ እንደያዘ ቁጢጥ ካለበት ብድግ ሲል እንቅስቃሴ ታየው፡፡ ተመልሶ ሸብረክ አለና እንዳጎነበሰ አሻግሮ ተመለከተ፡፡
እየተንገዳገደች ቆም ራመድ እንደገና ቆም እያለች በኮረኮንቹ መንገድ
ተመልሳ ትመጣለች ሰካራሟ፡፡
“ተነሽ…” አለ ናትናኤል የምሥራችን ክንድ እየጎተተ፡፡ “ሰካሪሟ ከተደበቁበት የቆሻሻ ማጠራቀሚያ በርሜሎች ስር ወጥተው ፈጠን ብለው በዋናው መንገድ አቅጣጫ አመሩ፡፡
“ታዲያስ!” አለቻቸው ከፊት ለፊታቸው እየተወለካከፈች፣ እየተንገዳገደች የምትመጣው ሰካራም::“እስቲ ወንድም ብር ግፋ፡፡” አለችው ናትናኤልን ስትመለከት እጇን ወደፊት ዘርግታ፡፡
“ዞር በይ!” አላ ናትናኤል አልፏት ለመሄድ እየሞከረ:: ድንገት በዘረጋችው መዳፏ ውስጥ የጨበጠችውን ሲመለከት ግን መላ አካላቱን ደነዘዘው፡፡ : የምሥራች ከፊቷ የተደቀነውን ስታይ እንዳትጮህ የፈራች ይመስል የገባ አፏን በገዛ መዳፏ ግጥም አድርጋ ዘጋችው፡፡
“የማይሆን ነገር አትሞክር፡፡” ኣለች ሰካራሟ የያዘችውን ሽጉጥ ወደ
ሆዱ ገፋ አድርጋ፡፡ “ተነቃነቅ..ዘረግፍሃለሁ፡፡” ድንገት ፊቷን ወደ የምሥራች መለሰችው፡፡ “አንድ ዕድል እሰጥሻለሁ፤ ካልቨርት የት ነው?”
የሽጉጧን አፈሙዝ መለስ አድርጋ የምሥራች ላይ ደቀነችው፡ “ንገሪኝ ጊዜ
አትውሰጂ!”
“እኔ ኣላውቅም፡፡”
በእጁ የጨበጠው የምሥራች ክንድ ሲንቀጠቀጥ ተሰማው:: “ተኩሼ ሳልቀረድድሽ ንገሪኝ:: ካልቨርት የት ነው?' ሴትየዋ አፏን ሳትከፍት በጥርሶቿ መሃል ተናገረች፡፡
“አላውቅምኮ፡፡” የምሥራች ድምፅ እንደ ወፍ ትንፋሽ ሳሳ፡፡ፍርሃት ያንቀጠቅጣት ጀመር፡፡
ሴትየዋ አላመነቻም፡፡ ወደኋላ ጥቂት እርምጃዎች አፈገፈገች፡፡ ናትናኤል ያልጠበቀው ድምፅ ቡፍ አለ፡፡ የምሥራች እጁ ላይ ተልፈሰፈሰችበት... ለቀቃት። ዝልፍልፍ ብላ በስተቀኙ ተዘረጋች፡፡ ከፊት
ለፊቱ ሽጉጧን ደግናበት ከቆመችው ሴት ጋር ተፋጠጠ፡፡ ትንፋሹን ይዞ ጠበቃት፡፡ አእምሮው እርስበርሱ ተጣላበት፡፡ ሊፈነዳ ያሰበ ይመስል ማጅራቱ ሲወጠር ተሰማው:: ዘሎ ይነቃት? ወይስ መጨረሻውን በቆመበት ይቀበል?
ድንገት ፈገግ ያለች መሰለው.. ፈገግ አለች ሴትየዋ፡፡ ከኋላው የሩጫ ድምፅ
ተሰማው፡፡ ከፊት ለፊቱ ቆማ የነበረችው ሴት በፍጥነት የሽጉጧን አፈሙ
ወደ መሬት መለሰችና ከትከሻው ላይ አሻግራ በጨለማው ላይ አፈጠጠች
“ሩጥ!” አለችው በሹክሹክታ ወደጎን ትታው የሩጫው ድምፅ ወደመጣበት እየተራመደች፡፡ “ተዋትና ሩጥ፤” አለችው ድጋሚ ፊቷን መልሳ፡፡ የምሥራችን እየጎተተ ወደ ጥግ ሲሸሸግ ስታየው፡፡ “እሷን ተውና ሩጥ!”
ናትናኤል ሳይመልስላት የምሥራችን ብብቶቿ ውስጥ ገብቶ እየጎተታት ወደ ጥግ ሽሽግ አለ፡፡ መሬቱ ላይ ተንበርክኮ የምሥራችን ጭንቅላት ቀና አደረገና ትንፋሿን አዳመጠ፡፡ አለች፡፡ የምሥራች... የምሥራች...” ድምፁን ቀንሶ ተጣራ፡፡
እያኖቿን በትግል ፡ ገልጣ ተመለከተችው.. እየሞተች ነው...
እየቀዘቀዘች ነው… እያበቃች ነው... ሊያድናት እንደማይችል ተረዳ፡፡
“የምስራች ንገሪኝ ካልቨርት የት ነው ንገሪኝ! ሁላችንን ሳይጨርሱን በፊት ንገሪኝ?”
“ካልቨርት ዮ....ሴፍ” ከጉሮሮዋ የሚወጣው ድምፅ ሻከረበት፡፡
“አዎ ዮሴፍ ዮሴፍ፡ ካልቨርት የት ነው ያለው?”
ከወዲያ የሚሰማው የሩጫ ድምፅ እየቀረበው መጣ አንድ ሴት
ስታንጎራጉር ይሰማል.. በጨለማው ውስጥ..
ዮ....ሴፍ...” የምሥራች ድምፅ በጭንቀት እየተበጣጠሰ ተንጠባጠበ፡፡
“አዎ.... አዎ የት ነው?”
የሩጫው ድምፅ ቀረበ፡፡ ናትናኤል ጭንቅላቱን መልሶ ከጀርባው ተመለከተ፡፡ ሰካራሟ መሀል
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
...ከሩቅ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ በርሜሎች ሲመለከት ክንዷን ይዞ ወደዚያው ጎተታት፡፡አካባቢውን ባለበሰው የቆሻሻ ክምር ላይ ተሻግረሁ ከበርሜሎቹ ጀርባ ዞረው ሸብረክ ሸብረክ አሉ፡፡በስተግሪ ራቅ ብሎ መደዳውን ከተኮለኮሉት የመሸታ ቤቶች የሚወጣው ደብዛዛ ብርሃን አካባቢውን በድቅድቁ ጨለማ ከመዋጥ አድኖታል ወዲያ ማዶ አንድ የጭነት መኪና ቆሟል፡፡ በስተቀኝ የውሾች ጥል በጨለማ ውስጥ አስተጋባ፡፡ድምፃቸውን አጥፍተው ተጠባበቁ፡፡
ናትናኤል ቀና ሲል በጨለማው ውስጥ አንድ ነገር ውልብ ሲል ተመለከተ፡፡ ዓይኖቹን በሰፊው ከፍቶ በጨለማው ላይ አፈጠጠ፡፡ ድምፅ ተሰማው... እየቀረበች ስትመጣ ሲለያት በእፎይታ ትንፋሽን ለቀቀ።ሰካራም ሴት ነበረች:: እንደመንገዳገድ ትልና ወደፊት ትራመዳለች፡፡ ትንሽ ታንጎራጉርና ደግሞ ወደፊት ተራመዳለች፡፡ ብዙም ሳይቆይ ከሰካራሟ ጀርባ የሌሎች ሰዎች ሩጫ ተሰማ፡፡ ናትናኤል ከበርሜሎቹ ጀርባ ሳይወጣ ጭንቅላቱን ብቻ አቅንቶ ተመለከተ::
ሦስት ሰዎች እየተሯሯጡ በኮረኮንቹ መንገድ መጡ፡፡ በኮረኮንቾ
መንገድ ላይ እየተወለካከፉ ሲሮጡ ናትናኤል አዳኞቹ እንደሆኑ ገባው::
ሰካራሟ ሴትጋ እንደደረሱ ከሦስቱ አንደኛው የያዘውን ባትሪ መለስ አድርጎ
ፊቷ ላይ ቦግ እደረገባት፡፡
“ትዝታ እ.. እባላለሁ፡፡” አለች ሰካራሟ ኣይኖቿን ባትሪው ብርሃን በክንዷ ከልላ “ሀ! ሀ! ሀ! ከፈለግህ ደሞ እቤት እንሂድና::ባትሪውን ያበራባት ሰው ትቷት ከጓደኞቹ ጋር ወደፊት ቀጠለ።
ሦስቱ ሰዎች ወደ ቆሻሻ ማጠራቀሚያዎቹ ሲደርሱ ትንሽ ሲቀራቸው ቆም አሉና ተነጋገሩ፡፡ ወዲያው ሁለቱ በስተቀኝ ታጥፈው በጨለማው ውስጥ ሲሰወሩ ባትሪ የያዘው ሰው በበርሜሎቹ ኣቅጣጫ አመራ፡፡
ናትናኤል አብራው የተደበቀችውን የካልቨርትን ወዳጅ ጠረጠራት፡፡
ብትጮህስ? ብትጣራና ብታሲዘውስ? እዚሁ ቆሻሻ መጣያ በርሜል : ስር
ደፍተውት ሊሄዱ አይደል? ፈጠን ብሎ ቀኝ እጁን በትከሻዋ አሳልፎ አፏን
አፈናትና በግራ እጁ የያዘውን የቢላ ጫፍ አንገቷ ስር ሽጎጠው፡፡
“ትንፍሽ እንዳትይ… ፊቱን ከማዞሩ በፊት ይሄ ቢላ ማጅራትሽ ነው የሚደርሰው፡፡” አላት ዓይኖቹን በበርሜሎቹ አቅጣጫ ቀሮጠው ሰው ላይ ተክሎ፡፡
ሳትነቃነቅ አይኖቿን ብቻ ኣቅንታ በጭንቀት ተመለከተችው::እንገቷ ስር የተሸጎጠው የቢላ : ስሎት ለስላሳ ቆዳዋን እንደ ምላጭ ሲሰነጥቀው ተሰማት::
ሰውየው ወደ በርሜሎቹ እየተጠጋ በመጣ ቁጥር በደመነፍስ ያወቀና የተረዳ ይመስል ፍጥነቱን ቀንሶ የባትሪውን ብርሃን እንደ ነብር ጅራት ከወዲያ ወዲህ እያላጋ ዙሪያውን እየፈትሽ በዝግታ ይራመድ ጀመር፡፡ እየቀረባቸው ሲመጣ ናትናኤል በበርሜሎቹ አናት ላይ ተመለከተው።በግራው ባትሪውን እንደጨበጠ በስተቀኝ የኮት ኪሱ ውስጥ የጨመረውን እጁን ሲመለከት ስውየው መሣሪያ እንደያዘ ናትናኤል ተረዳ፡፡ በየምሥራች አፍ ላይ የጫነውን የቀኝ እጁን ጠበቅ አደረገና በግራው የያዘውን ቢላ ከአንገቷ ስር አውጥቶ ይዞ ተዘጋጀ፡፡ ተጠባበቀ፡፡ ከበርሜሎቹ ዙሪያ
የፈሰሰው ቆሻሻ ላይ ሲረግጥ የአዳኙ ኮቴ ኮሽታ ተሰማው። ሲጠጋውና
ሲቀርበው ሲደርስበት ተወርውሮ ቢላውን ሊሰካበት ተዘጋጀ፡፡ ሰውየው
ድንገት ቆም አለ፡፡ ያመነታ መስለ ባትሪውን ዞር አድርጎ በበርሜሎቹ ላይ
እበራ፡፡ የባትሪውን ብርሃን በዙሪያው አወናጨፈው፡፡ ወዲያው ፊቱን መልሶ
በኮረኮንቹ መንገድ ወደፊት ቀጠለ፡፡
ሰውየው ከራቀ ወዲያ ነበር ናትናኤል ለመተንፈስ የደፈረው።የምሥራችን አፍ ለቀቀና ቀና አደረጋት፡፡
“አይዞሽ አትፍሪ፤ ልጎዳሽ አልፈልግም:: እመኚኝ፡፡ ከዚህ በላይ ምን ማረጋገጫ ነው የምትፈልጊው?” አለ ትከሻዋን በሁለት እጆቹ ይዞ እየነቀነቀ፡፡ “በይ ተነሺ… ሳንቻኮል በእርጋታ እየተራመድን ወደ ዋናው መንገድ እንውጣለን፡፡ ለመሮጥ ወይ ለመጮህ ብትሞክሪ ግን ምርጫ አይኖረኝም::”
“አልሮጥም::” አለች ፊቷን መልሳ በፍርሃት እየተመለከተችው::
ናትናኤል የምሥራችን ክንድ እንደያዘ ቁጢጥ ካለበት ብድግ ሲል እንቅስቃሴ ታየው፡፡ ተመልሶ ሸብረክ አለና እንዳጎነበሰ አሻግሮ ተመለከተ፡፡
እየተንገዳገደች ቆም ራመድ እንደገና ቆም እያለች በኮረኮንቹ መንገድ
ተመልሳ ትመጣለች ሰካራሟ፡፡
“ተነሽ…” አለ ናትናኤል የምሥራችን ክንድ እየጎተተ፡፡ “ሰካሪሟ ከተደበቁበት የቆሻሻ ማጠራቀሚያ በርሜሎች ስር ወጥተው ፈጠን ብለው በዋናው መንገድ አቅጣጫ አመሩ፡፡
“ታዲያስ!” አለቻቸው ከፊት ለፊታቸው እየተወለካከፈች፣ እየተንገዳገደች የምትመጣው ሰካራም::“እስቲ ወንድም ብር ግፋ፡፡” አለችው ናትናኤልን ስትመለከት እጇን ወደፊት ዘርግታ፡፡
“ዞር በይ!” አላ ናትናኤል አልፏት ለመሄድ እየሞከረ:: ድንገት በዘረጋችው መዳፏ ውስጥ የጨበጠችውን ሲመለከት ግን መላ አካላቱን ደነዘዘው፡፡ : የምሥራች ከፊቷ የተደቀነውን ስታይ እንዳትጮህ የፈራች ይመስል የገባ አፏን በገዛ መዳፏ ግጥም አድርጋ ዘጋችው፡፡
“የማይሆን ነገር አትሞክር፡፡” ኣለች ሰካራሟ የያዘችውን ሽጉጥ ወደ
ሆዱ ገፋ አድርጋ፡፡ “ተነቃነቅ..ዘረግፍሃለሁ፡፡” ድንገት ፊቷን ወደ የምሥራች መለሰችው፡፡ “አንድ ዕድል እሰጥሻለሁ፤ ካልቨርት የት ነው?”
የሽጉጧን አፈሙዝ መለስ አድርጋ የምሥራች ላይ ደቀነችው፡ “ንገሪኝ ጊዜ
አትውሰጂ!”
“እኔ ኣላውቅም፡፡”
በእጁ የጨበጠው የምሥራች ክንድ ሲንቀጠቀጥ ተሰማው:: “ተኩሼ ሳልቀረድድሽ ንገሪኝ:: ካልቨርት የት ነው?' ሴትየዋ አፏን ሳትከፍት በጥርሶቿ መሃል ተናገረች፡፡
“አላውቅምኮ፡፡” የምሥራች ድምፅ እንደ ወፍ ትንፋሽ ሳሳ፡፡ፍርሃት ያንቀጠቅጣት ጀመር፡፡
ሴትየዋ አላመነቻም፡፡ ወደኋላ ጥቂት እርምጃዎች አፈገፈገች፡፡ ናትናኤል ያልጠበቀው ድምፅ ቡፍ አለ፡፡ የምሥራች እጁ ላይ ተልፈሰፈሰችበት... ለቀቃት። ዝልፍልፍ ብላ በስተቀኙ ተዘረጋች፡፡ ከፊት
ለፊቱ ሽጉጧን ደግናበት ከቆመችው ሴት ጋር ተፋጠጠ፡፡ ትንፋሹን ይዞ ጠበቃት፡፡ አእምሮው እርስበርሱ ተጣላበት፡፡ ሊፈነዳ ያሰበ ይመስል ማጅራቱ ሲወጠር ተሰማው:: ዘሎ ይነቃት? ወይስ መጨረሻውን በቆመበት ይቀበል?
ድንገት ፈገግ ያለች መሰለው.. ፈገግ አለች ሴትየዋ፡፡ ከኋላው የሩጫ ድምፅ
ተሰማው፡፡ ከፊት ለፊቱ ቆማ የነበረችው ሴት በፍጥነት የሽጉጧን አፈሙ
ወደ መሬት መለሰችና ከትከሻው ላይ አሻግራ በጨለማው ላይ አፈጠጠች
“ሩጥ!” አለችው በሹክሹክታ ወደጎን ትታው የሩጫው ድምፅ ወደመጣበት እየተራመደች፡፡ “ተዋትና ሩጥ፤” አለችው ድጋሚ ፊቷን መልሳ፡፡ የምሥራችን እየጎተተ ወደ ጥግ ሲሸሸግ ስታየው፡፡ “እሷን ተውና ሩጥ!”
ናትናኤል ሳይመልስላት የምሥራችን ብብቶቿ ውስጥ ገብቶ እየጎተታት ወደ ጥግ ሽሽግ አለ፡፡ መሬቱ ላይ ተንበርክኮ የምሥራችን ጭንቅላት ቀና አደረገና ትንፋሿን አዳመጠ፡፡ አለች፡፡ የምሥራች... የምሥራች...” ድምፁን ቀንሶ ተጣራ፡፡
እያኖቿን በትግል ፡ ገልጣ ተመለከተችው.. እየሞተች ነው...
እየቀዘቀዘች ነው… እያበቃች ነው... ሊያድናት እንደማይችል ተረዳ፡፡
“የምስራች ንገሪኝ ካልቨርት የት ነው ንገሪኝ! ሁላችንን ሳይጨርሱን በፊት ንገሪኝ?”
“ካልቨርት ዮ....ሴፍ” ከጉሮሮዋ የሚወጣው ድምፅ ሻከረበት፡፡
“አዎ ዮሴፍ ዮሴፍ፡ ካልቨርት የት ነው ያለው?”
ከወዲያ የሚሰማው የሩጫ ድምፅ እየቀረበው መጣ አንድ ሴት
ስታንጎራጉር ይሰማል.. በጨለማው ውስጥ..
ዮ....ሴፍ...” የምሥራች ድምፅ በጭንቀት እየተበጣጠሰ ተንጠባጠበ፡፡
“አዎ.... አዎ የት ነው?”
የሩጫው ድምፅ ቀረበ፡፡ ናትናኤል ጭንቅላቱን መልሶ ከጀርባው ተመለከተ፡፡ ሰካራሟ መሀል
👍1
ኮረኮንቹ ላይ እየተንገዳገደች ወደፊት ራመድ ትልና እንደገና ቆም ብላ ታንጎራጉራለች..
“ንገሪኝ የምሥራች ካልቨርት የት ነው?”
“ዮሴፍ… እ… እማዬጋ” አየር ለመሳብ ስትታገል ደረቷ ሽቅብ ተስቀለ፡፡
“የት... የት?”
“እእማዬጋ ድሬዳዋ” የጀመረችውን ከመጨረሷ በፊት ሰውነቷ ተዝለፍልፎ ክንዱ ላይ ወደቀች፡፡ ናትናኤል ቀና ሊያደርጋት ሞከረ። አብቅታለች። ሰውነቱ ከቁጥጥሩ ውጭ ሆነበት ከተንበረከከበት ብድግ ብሎ ለመሮጥ ተዘጋጀ፡፡ ከወዲያ እየሮጠ የሚመጣው ሰው ሰካራሟጋ ሲደርስ በጨለማው ውስጥ ታየው፡፡ አዳኙ ወደ ሴትየዋ እንደደረሰ በግራው የያዘወን ባትሪ ፊቷ ላይ ቦግ አደረገውና ወዲያው ወደጎን ገፍተር አድርጓት አለፈ... ከመቅፅበት ባትሪውን ወደጎን መለስ አድርጎ ናትናኤል ላይ ሲተክለው ናትናኤል ቁጢጥ ካለበት መነሳት ተሳነው፡፡
አዳኙ ቀኝ እጁን ከኪሱ መንጭቆ አውጥቶ ሽጉጡን ደግኖ ይዞ
ተጠጋው፡፡
“አገኘሁህ!” አለ ወደ ውጭ ተንፍሶ ወዲያው ከናትናኤል ጎን የተዘረጋውን የምሥራችን ሰውነት ሲመለከት አይኖቹ ከየጉድጓዶቻቸው ወጡ፡፡ “ገደልካት?!” አለ የሚያየውን ማመን አቅቶት ኣፉን በድንጋጤ ከፍቶ::
“እኔ አይደለሁም! እኔ አይደለሁም!” አለ ናትናኤል ጭንቅላቱን በጭንቀት እያርገፈገፈ::
ሰውየው በጥላቻ ቁልቁል ተመልክተው:: “ከሃዲ! ያንተ ዓይነቶቹ ውሾች ናቸው ለባርነት የዳረጉን ዝርክርክ!” ሽጉጡን አንስቶ አነጣጠረበት፡፡
ናትናኤል ጉሮሮው እንደኮረት ሲወጠርበት ልሳኑ ሲከዳው… ሁለት እጆቹን ወደፊት ዘርግቶ አውለበለባቸው:: አርፈህ በሰላም ኑር…እንደ እሳት እራት ወደ ፍሙ… ተጠንቀቅ…የሽጉጡን አፈሙዝ ተመለከተው… እንደ አጋንንት ከፊቱ ተደቅኖ ሲያየው ሰውነቱ ፈሰስ... አይኖቹን ጨፈናቸው…
ርብቃ! …ቡፍ! ሲተኮስ ተሰማው፡፡ የትጋ እንደተመታ አልታወቀውም። እላዩ ላይ ወደቀበት፡፡ ዓይኖቹን ገልጦ ግራ ተጋቡ፡፡ አዳኙ እላዩ ላይ ተዘርግፎበታል። ዓይኖቹ ከየጎሬአቸው ወጥተው ተጎልጉለዋል፡፡ በጭንቅ የገጠመው ጥርሱና ከጉሮሮው የሚወጣው ሲር ሲር የሚለው ድምፅ:..
ባንድ ወገን ከአፉ ቡልቅ ብሎ የወጣ ደም ደረቱ ላይ ሲረጭ... ናትናኤል
ሰውየውን ከላዩ ገፍትሮ አገለለው፡፡ ቁጢጥ ባለበት ጥይት የበሳው ገላውን
አዳመጠ፡፡ የለም፡፡ ከተቀመጠበት ተነሳ፡፡
ራቅ ብላ በቀኟ ያንጠለጠለችውን የሽጉጥ አፈሙዝ ወደ መሬቱ መልሳ : ቆማለች፡፡ ፈገግ አለችለት፡፡ ጀርባውን ለግድግዳው እንደሰጠ ተመልከታት፡፡
“ሩጥ፡፡” አለችው ፈገግ ብላ።
ሮጠ፡፡
ሮጠ ናትናኤል፡፡ በኮረኮንቹ እድርጎ ቁልቁል በመጣበት ቀጭን መንገድ ሽቅብ በረረ፡፡ ከኋላው የተከተለው አጋንንት እንዳለ ሁሉ በጨለማው
ውስጥ እጆቹን ወደፊት ዘርግቶ በነነ፡፡ በአካባቢው ድምፅ አልነበረም::
ጠባቧን የኮረኮንች መንገድ ጨርሶ ከመውጣቱ በፊት ብቻ ከጀርባው ሳቅ
አጀበው:: የሴት ሳቅ የሰካራም ሳቅ
ሃ...ሃ...ሃ. …ሃ...ሂ....ሂ... ሂ!”.....
💫ይቀጥላል💫
“ንገሪኝ የምሥራች ካልቨርት የት ነው?”
“ዮሴፍ… እ… እማዬጋ” አየር ለመሳብ ስትታገል ደረቷ ሽቅብ ተስቀለ፡፡
“የት... የት?”
“እእማዬጋ ድሬዳዋ” የጀመረችውን ከመጨረሷ በፊት ሰውነቷ ተዝለፍልፎ ክንዱ ላይ ወደቀች፡፡ ናትናኤል ቀና ሊያደርጋት ሞከረ። አብቅታለች። ሰውነቱ ከቁጥጥሩ ውጭ ሆነበት ከተንበረከከበት ብድግ ብሎ ለመሮጥ ተዘጋጀ፡፡ ከወዲያ እየሮጠ የሚመጣው ሰው ሰካራሟጋ ሲደርስ በጨለማው ውስጥ ታየው፡፡ አዳኙ ወደ ሴትየዋ እንደደረሰ በግራው የያዘወን ባትሪ ፊቷ ላይ ቦግ አደረገውና ወዲያው ወደጎን ገፍተር አድርጓት አለፈ... ከመቅፅበት ባትሪውን ወደጎን መለስ አድርጎ ናትናኤል ላይ ሲተክለው ናትናኤል ቁጢጥ ካለበት መነሳት ተሳነው፡፡
አዳኙ ቀኝ እጁን ከኪሱ መንጭቆ አውጥቶ ሽጉጡን ደግኖ ይዞ
ተጠጋው፡፡
“አገኘሁህ!” አለ ወደ ውጭ ተንፍሶ ወዲያው ከናትናኤል ጎን የተዘረጋውን የምሥራችን ሰውነት ሲመለከት አይኖቹ ከየጉድጓዶቻቸው ወጡ፡፡ “ገደልካት?!” አለ የሚያየውን ማመን አቅቶት ኣፉን በድንጋጤ ከፍቶ::
“እኔ አይደለሁም! እኔ አይደለሁም!” አለ ናትናኤል ጭንቅላቱን በጭንቀት እያርገፈገፈ::
ሰውየው በጥላቻ ቁልቁል ተመልክተው:: “ከሃዲ! ያንተ ዓይነቶቹ ውሾች ናቸው ለባርነት የዳረጉን ዝርክርክ!” ሽጉጡን አንስቶ አነጣጠረበት፡፡
ናትናኤል ጉሮሮው እንደኮረት ሲወጠርበት ልሳኑ ሲከዳው… ሁለት እጆቹን ወደፊት ዘርግቶ አውለበለባቸው:: አርፈህ በሰላም ኑር…እንደ እሳት እራት ወደ ፍሙ… ተጠንቀቅ…የሽጉጡን አፈሙዝ ተመለከተው… እንደ አጋንንት ከፊቱ ተደቅኖ ሲያየው ሰውነቱ ፈሰስ... አይኖቹን ጨፈናቸው…
ርብቃ! …ቡፍ! ሲተኮስ ተሰማው፡፡ የትጋ እንደተመታ አልታወቀውም። እላዩ ላይ ወደቀበት፡፡ ዓይኖቹን ገልጦ ግራ ተጋቡ፡፡ አዳኙ እላዩ ላይ ተዘርግፎበታል። ዓይኖቹ ከየጎሬአቸው ወጥተው ተጎልጉለዋል፡፡ በጭንቅ የገጠመው ጥርሱና ከጉሮሮው የሚወጣው ሲር ሲር የሚለው ድምፅ:..
ባንድ ወገን ከአፉ ቡልቅ ብሎ የወጣ ደም ደረቱ ላይ ሲረጭ... ናትናኤል
ሰውየውን ከላዩ ገፍትሮ አገለለው፡፡ ቁጢጥ ባለበት ጥይት የበሳው ገላውን
አዳመጠ፡፡ የለም፡፡ ከተቀመጠበት ተነሳ፡፡
ራቅ ብላ በቀኟ ያንጠለጠለችውን የሽጉጥ አፈሙዝ ወደ መሬቱ መልሳ : ቆማለች፡፡ ፈገግ አለችለት፡፡ ጀርባውን ለግድግዳው እንደሰጠ ተመልከታት፡፡
“ሩጥ፡፡” አለችው ፈገግ ብላ።
ሮጠ፡፡
ሮጠ ናትናኤል፡፡ በኮረኮንቹ እድርጎ ቁልቁል በመጣበት ቀጭን መንገድ ሽቅብ በረረ፡፡ ከኋላው የተከተለው አጋንንት እንዳለ ሁሉ በጨለማው
ውስጥ እጆቹን ወደፊት ዘርግቶ በነነ፡፡ በአካባቢው ድምፅ አልነበረም::
ጠባቧን የኮረኮንች መንገድ ጨርሶ ከመውጣቱ በፊት ብቻ ከጀርባው ሳቅ
አጀበው:: የሴት ሳቅ የሰካራም ሳቅ
ሃ...ሃ...ሃ. …ሃ...ሂ....ሂ... ሂ!”.....
💫ይቀጥላል💫
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
.....አኔም በሩ ከተዘጋ በኋላ ይዛው የነበረውን እምባዋን ለቅቃ እየተንሰቀሰቀች ማልቀስ ጀመረች::
ወደ ታችኛው የከተማው ክፍል በ10ኛው ጓዳና ላይ መኪናዋን የምታሽከረክረው ኒኪ ሆዷ ድረስ ዘልቆ የሚሰማ የንዴት እና የሀዘን ስሜት ውስጥ ትገኛለች። አለ
አይደል በደም ሥሯ ደም ሳይሆን እርጎ
የሚዘዋወርባት ይመስል ሁለመናዋን የሚስማት የሚቆመጥጥ ነገር ብቻ
ነው። አንዴ ለእሷ ታዝናለች፤ ደግሞ የተዋረደች ይመስላታል፡፡ ደግሞ
ንዴት እና ፀፀት ተቀላቅሎ ይሰማታል።
ስለ አኔ ባል ለአኔ የነገረቻት ነገር ትክክል ነው። ባሏ ምንም ያህል ለጋስ እና አማላይ ቢሆንም ያው ደካማን የሚያጠቃ በጥባጭ ነገር ነው። በጥባጭ
ሰው ደግሞ መቼም አይለወጥም። ይህንን ነገር ለአኔ ብትነግራት አሁን ላይ
እንደማትሰማት ይገባታል። ምክንያቱም ከአሁን በኋላ አኔ ኒኪን እንደ ሀኪሟ አይደለም የምታያት። አኔ ኒኪን እንዴት ነው የምታያት? ብላ ራሷን ጠየቀች፡፡ “እንደ ጓደኛዋ? ምናልባት እንደ ፍቅረኛዋ? ምናልባት ከባሏ ልትነጥላት ቆርጣ እንደተነሳች ሴት?”
አኔን በዚህ መልኩ ማናገር አልነበረባትም።
ይሄው አኔ በግልፅ ባይሆንም ኒኪ ቀድማ ብዙ ስለቀረበቻት ይህንን ተናግራት አይደል “አንቺ እንደ ቴራፒስት አይደለም ለእኔ ደንታ ያለሽ፡፡ ይሄንን ደግሞ ሁለታችንም እናውቀዋለን!” ብላታለች። ግን የዶውግን ከትዳር ውጪ ስላለው ግንኙነት እንዴት ልታውቅ ቻለች? አኔ እንዴት ስለ እዚህ ጉዳይ ማወቅ ቻለች? ይህንን ጉዳይ የሚያውቁት ደግሞ ጓደኛዋ ግሬቸን እና ዶፎ ናቸው፡፡ እነርሱ ደግሞ በፍፁም ይህንን ነገር ለማንም እንደማያወሩት ታውቃለች፡፡
የሚሰማት የሚያስጠላ ስሜት ሲጨምር በመኪናው መስኮት ወደ ውጪ ተመለከተች፡፡ አራት ቤት አልባ የሆኑ ሰዎች ከቲያትር ቤቱ መግቢያ በር
ላይ ተደርድረው ቁጭ ብለዋል፡፡ ከእነርሱ ውስጥ አንዱ ባዶ እና ተስፋ አልባ
ስሜት ውስጥ ሆኖ ወደ እሷ አይኑን ጎልጉሎ ይመለከታታል። በሱስ ናውዟል፤ ያስታውቃል፡፡ የሆነ የሀዘኔታ ስሜት እንዲሰማት ጠበቀች። የለም፡፡ ይሄንን ስሜቷን ያቺ ሸርሙጣ የሟች ባሏ ሩሲያዊቷ ውሽማ አጥፍታባታለች፡፡
የሆነ ልቧ ውስጥ ያለውን ያቺን የዋህዋን
ኒኪን ይህቺ ሴት ገድላባታለች። ወይንም ይሄ ነገሯ አልሞተም፤ በቃ ነዳጅ ምናምን አልቆበት ነው። ምናልባት አንድ ቀን የፍቅር እና ለሰዎች ያላት የመልካም ስሜቷ ነዳጇ መልሶ ሙሉ ሲሆን የሀዘኔታ ስሜቷን መልሳ ታገኘው ይሆናል።
ምናልባት!
ወይም ደግሞ ጨርሶም ላይመጣ ይችላል።
የመንገዱ እግረኛ ማቋረጫ ላይም አንዲት በመሀከለኛ ዕድሜ ላይ
የምትገኝ ሌላ ሴትን ተመለከተች፡፡ ይህቺ ሴትም ያኔ ዶፎ ቬኒስ ውስጥ የሚገኘውን ክሊኒክ ሲያስጎበኛት እንዳየቻቸው ሁለቱ ጎረምሶች አጥንቷ ገጥጦ ወጥቷል፡፡ መልካም አረንጓዴ ነው። ዶፎ ክሮክዳይል ይባላል። አዲስ የመጣ አደንዛዥ ዕፅ ነው ብሎ የነገራትን ነገር አስታወሰች፡፡
ያኔ ክሊኒኩ ውስጥ ላየቻቸው ሁለቱ ጎረምሶች ሀዘኔታ ተሰምቷት ነበር፡፡
አሁን ግን ይሄው ባዶ ናት፤ ምንም ነገር አይሰማትም። ምናልባት ከአኔ ጋር
ስታወራ የተቀበለችው ውርደት ይህንን ውስጧ የቀረውን እንጥፍጣፊ
የሀዘኔታ ስሜትን አጥፍቶባት ይሆን?
ምንም ነገር ማሰብ አቆመች እና ዝም ብላ ወደ ቤቷ አቅጣጫ መኪናዋን
ማሽከርከር ጀመረች። ቤቷ ስትደርስ ደጃፏ ላይ ሁለት ፖሊሶች የፖሊስ
መኪና ውስጥ ተቀምጠው አገኘቻቸው። ፖሊሶቹ ትላንትና ማታ መርማሪ
ፖሊስ ጉድማን የእሷን እምቢታ ሳይቀበል ቀርቶ እንዲጠብቋት የመደበላት
ፖሊሶች ናቸው፡፡
ትላንትና ማታ የእሱ መኪና ውስጥ ቁጭ ብለው እጁን ታፋዋ ላይ አድርጎ “ጥበቃ ያስፈልግሻል” ብሏት ነበር።
“ምንም አይነት ጥበቃ አልፈልግም”
“ኒኪ ጥበቃውን አንቺ ስለፈለግሽው ሳይሆን የምመድብልሽ ሥራዬ
ስለሆነ ነው እሺ” ብሎ ሲናገራት ውስጧን ደስ የሚል ነገር ተሰምቷት
ነበር።
“እኔ ያንተን ጥበቃ ባልፈልግስ?” ብላው ነበር። የእሷን እጅ የት አድርጋ ፀታወራው እንደነበር አስታውሳም።
እንደርሱ ከሆነማ እተውሻለሁ ዶክተር” ብሏት ነበር ጉድማን ማዕረጓን ልክ እንደ ስድብ የተጠቀመበት።
የፖሊሶቹ ቤቷ አጠገብ መገኘት ጉድማን ትላንትና ማታ እሷን ለማማለል ሳይሆን ስለ ጥበቃ ያወራው ነገር የእውነቱን መሆኑን እንድትረዳ አደረጋት። ግትርነት የምትወዳቸው የወንዶች ፀባይ ነው መሰለኝ ግትር ወንዶች ደስ ይሏታል። ምንም እንኳን መጨረሻቸው ባልጠበቀችው መልኩ ቢያበቃም ባሏ ዶውግም እንደዚያ ነበር።
አይኗ በእምባ ሲሞላ ኒኪ ተናደደች እና እምባዋን ውጣ፣ መኪናዋንም አቁማ ወደ ቤቷ ገባች። የቤቷን መብራት አብርታ እና ጫማዋን ወርውራ አውልቃ ወደ ማብሰያ ክፍሏ አመራች። አዲስ የገዛችውን ቦርሳዋን ከማብሰያው ክፍል ባልኮኒ ላይ አስቀመጠች። የማታው የዞረ ድምር እስከ አሁን ባይለቃትም ፍሪጂ ውስጥ ያስቀመጠችውን ቨርጅን ሜሪ መጠጥ
ብርጭቆዋን ሞላች። የባልኮኒው ወንበር ላይ ቁጭ እንዳለችም ላፕቶፕዋን
ከፈተች እና ኢ ሜይሏን ተመለከተች፡፡
ምናልባት አኔ ኢ ሜይል ልካ ከሆነ ብላ ነበር ለፕቶፕዋን የከፈተችው።
ከአኔ ግን ምንም የተላከ ኢ ሜይል አላገኘችም።
ሌላ የተላከላት ኢ ሜይል ስለበነረም ከፈተችው። የማታውቀው ኢ ሜይሉን የላከላት ግለሰብ 'ትላንትና ማታ አይቼሻለሁ! በሚል ርዕስ ሥር
ትላንትና ማታ ከጉድማን ጋር አብረው የነበሩበት የዳን ታና ሬስቶራንት ፎቶ
ለጥፏል። ከሆቴሉ ሥር ያለው ሁለተኛው ፎቶ ደግሞ የእሷን ከአንገት በላይ
ያላ ፎቶን ከአንዲት ራቁቷን ከምትወዛወዝ የካርቶን ቪዲዩ ላይ በፎቶ ሾን አያይዞታል። ከፎቶውም በታች “አንቺ ሸርሙጣ እገድልሻለሁ!” የሚል
ማስፈራሪያ ተፅፎበታል።
ኒኪ ይህንን ካየች በኋላ ድንገተኛ ድንጋጤ እና ፍርሃት ወረራት፡፡
በመቀጠልም ድንዝዝ ያለ ስሜት ውስጥ ገብታ ቁጭ አለች።
ስሜቷ ደንዝዞ ብትቀመጥም ጎበዙ አዕምሮዋ የሆነ ነገር ማድረግ እንዳለበት ይወተውታት ጀመረ። ይሄ ቀልድ አይደለም። ይሄ የግድያ ዛቻ ነው፡፡ ለዚያውም የእሷን እያንዳንዱን እንቅስቃሴዎቿን ከሚያውቅ ሰው
ትላንትና ማታ ዳና ሬስቶራንት ውስጥ ከማን ጋር እንደነበረች ሁሉ
ከሚያውቅ ሰው ነው ማስፈራሪያው የተላከላት። ስለዚህ ነገሩን ለፖሊስ
ማሳወቅ ይኖርባታል። አሊያም ደግሞ ለጉድማን ልትነግረው ይገባል።
ግን ደግሞ ትንሽ አመነታች፡ ለመልከመልካሙ መርማሪ ፖሊስ
ጉድማን ነገሩን ማሳወቅ እሱን ይበልጥ ወደ እሷ ህይወት እንዲገባ ማድረግ
አይሆንምን?
ልጠብቅሽ ነው በሚል ሀሳብ ከእሷ ጋር እንዲጣበቅ ምክንያት ማቀበል
አይሆንም?
ግማሽ እሷነቷ ለመርማሪው ነገሩን አሳውቂ ሲላት፣ ግማሽ እና ብልሁ
ሌላኛው እሷነቷ ግን ይህ ትክክል እንዳልሆነ ነገራት።
ጉድማን መልካም ሰው ነው፤ ችግሩን ለመፍታት አስፈላጊውን ጥረት ሁሉ ያደርጋል። ግን ደግሞ ባልደረባው የሰይጣን ቁራጩ ጆንሰን አብሮት
የሚሰራ አጋሩ እስከሆነ ድረስ ሁለቱም የግድ የእሷን ጉዳይ ይመለከቱታል
ማለት ነው። ይሄ የእሱ አጋርነት ደግሞ የሊዛን እና የትሬይን ገዳይ እንዲሁም ደግሞ እሷን ጭምር በመኪና ሊገድላት የሞከረ ሰውን ይዞ ለፍርድ ማቅረብ ያቃተው እንደሆነ እያየችው ነው።
ለማንኛውም ህይወቷ አደጋ ላይ ነው፣ ኒኪ ጥበቃ ያስፈልጋታል።ከጥበቃው በላይ ደግሞ መልስ ትፈልጋለች፡፡ የምትፈልገው መልስ ደግሞ ስለ ግድያዎቹ ብቻ አይደለም። የዶውግን ክህደት ካወቀችበት ጊዜ ጀምሮ
በዋናነት የእሷን ህይወትን መርዞባት እስከ አሁን ድረስ ውስጧን ለሚያደማት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
.....አኔም በሩ ከተዘጋ በኋላ ይዛው የነበረውን እምባዋን ለቅቃ እየተንሰቀሰቀች ማልቀስ ጀመረች::
ወደ ታችኛው የከተማው ክፍል በ10ኛው ጓዳና ላይ መኪናዋን የምታሽከረክረው ኒኪ ሆዷ ድረስ ዘልቆ የሚሰማ የንዴት እና የሀዘን ስሜት ውስጥ ትገኛለች። አለ
አይደል በደም ሥሯ ደም ሳይሆን እርጎ
የሚዘዋወርባት ይመስል ሁለመናዋን የሚስማት የሚቆመጥጥ ነገር ብቻ
ነው። አንዴ ለእሷ ታዝናለች፤ ደግሞ የተዋረደች ይመስላታል፡፡ ደግሞ
ንዴት እና ፀፀት ተቀላቅሎ ይሰማታል።
ስለ አኔ ባል ለአኔ የነገረቻት ነገር ትክክል ነው። ባሏ ምንም ያህል ለጋስ እና አማላይ ቢሆንም ያው ደካማን የሚያጠቃ በጥባጭ ነገር ነው። በጥባጭ
ሰው ደግሞ መቼም አይለወጥም። ይህንን ነገር ለአኔ ብትነግራት አሁን ላይ
እንደማትሰማት ይገባታል። ምክንያቱም ከአሁን በኋላ አኔ ኒኪን እንደ ሀኪሟ አይደለም የምታያት። አኔ ኒኪን እንዴት ነው የምታያት? ብላ ራሷን ጠየቀች፡፡ “እንደ ጓደኛዋ? ምናልባት እንደ ፍቅረኛዋ? ምናልባት ከባሏ ልትነጥላት ቆርጣ እንደተነሳች ሴት?”
አኔን በዚህ መልኩ ማናገር አልነበረባትም።
ይሄው አኔ በግልፅ ባይሆንም ኒኪ ቀድማ ብዙ ስለቀረበቻት ይህንን ተናግራት አይደል “አንቺ እንደ ቴራፒስት አይደለም ለእኔ ደንታ ያለሽ፡፡ ይሄንን ደግሞ ሁለታችንም እናውቀዋለን!” ብላታለች። ግን የዶውግን ከትዳር ውጪ ስላለው ግንኙነት እንዴት ልታውቅ ቻለች? አኔ እንዴት ስለ እዚህ ጉዳይ ማወቅ ቻለች? ይህንን ጉዳይ የሚያውቁት ደግሞ ጓደኛዋ ግሬቸን እና ዶፎ ናቸው፡፡ እነርሱ ደግሞ በፍፁም ይህንን ነገር ለማንም እንደማያወሩት ታውቃለች፡፡
የሚሰማት የሚያስጠላ ስሜት ሲጨምር በመኪናው መስኮት ወደ ውጪ ተመለከተች፡፡ አራት ቤት አልባ የሆኑ ሰዎች ከቲያትር ቤቱ መግቢያ በር
ላይ ተደርድረው ቁጭ ብለዋል፡፡ ከእነርሱ ውስጥ አንዱ ባዶ እና ተስፋ አልባ
ስሜት ውስጥ ሆኖ ወደ እሷ አይኑን ጎልጉሎ ይመለከታታል። በሱስ ናውዟል፤ ያስታውቃል፡፡ የሆነ የሀዘኔታ ስሜት እንዲሰማት ጠበቀች። የለም፡፡ ይሄንን ስሜቷን ያቺ ሸርሙጣ የሟች ባሏ ሩሲያዊቷ ውሽማ አጥፍታባታለች፡፡
የሆነ ልቧ ውስጥ ያለውን ያቺን የዋህዋን
ኒኪን ይህቺ ሴት ገድላባታለች። ወይንም ይሄ ነገሯ አልሞተም፤ በቃ ነዳጅ ምናምን አልቆበት ነው። ምናልባት አንድ ቀን የፍቅር እና ለሰዎች ያላት የመልካም ስሜቷ ነዳጇ መልሶ ሙሉ ሲሆን የሀዘኔታ ስሜቷን መልሳ ታገኘው ይሆናል።
ምናልባት!
ወይም ደግሞ ጨርሶም ላይመጣ ይችላል።
የመንገዱ እግረኛ ማቋረጫ ላይም አንዲት በመሀከለኛ ዕድሜ ላይ
የምትገኝ ሌላ ሴትን ተመለከተች፡፡ ይህቺ ሴትም ያኔ ዶፎ ቬኒስ ውስጥ የሚገኘውን ክሊኒክ ሲያስጎበኛት እንዳየቻቸው ሁለቱ ጎረምሶች አጥንቷ ገጥጦ ወጥቷል፡፡ መልካም አረንጓዴ ነው። ዶፎ ክሮክዳይል ይባላል። አዲስ የመጣ አደንዛዥ ዕፅ ነው ብሎ የነገራትን ነገር አስታወሰች፡፡
ያኔ ክሊኒኩ ውስጥ ላየቻቸው ሁለቱ ጎረምሶች ሀዘኔታ ተሰምቷት ነበር፡፡
አሁን ግን ይሄው ባዶ ናት፤ ምንም ነገር አይሰማትም። ምናልባት ከአኔ ጋር
ስታወራ የተቀበለችው ውርደት ይህንን ውስጧ የቀረውን እንጥፍጣፊ
የሀዘኔታ ስሜትን አጥፍቶባት ይሆን?
ምንም ነገር ማሰብ አቆመች እና ዝም ብላ ወደ ቤቷ አቅጣጫ መኪናዋን
ማሽከርከር ጀመረች። ቤቷ ስትደርስ ደጃፏ ላይ ሁለት ፖሊሶች የፖሊስ
መኪና ውስጥ ተቀምጠው አገኘቻቸው። ፖሊሶቹ ትላንትና ማታ መርማሪ
ፖሊስ ጉድማን የእሷን እምቢታ ሳይቀበል ቀርቶ እንዲጠብቋት የመደበላት
ፖሊሶች ናቸው፡፡
ትላንትና ማታ የእሱ መኪና ውስጥ ቁጭ ብለው እጁን ታፋዋ ላይ አድርጎ “ጥበቃ ያስፈልግሻል” ብሏት ነበር።
“ምንም አይነት ጥበቃ አልፈልግም”
“ኒኪ ጥበቃውን አንቺ ስለፈለግሽው ሳይሆን የምመድብልሽ ሥራዬ
ስለሆነ ነው እሺ” ብሎ ሲናገራት ውስጧን ደስ የሚል ነገር ተሰምቷት
ነበር።
“እኔ ያንተን ጥበቃ ባልፈልግስ?” ብላው ነበር። የእሷን እጅ የት አድርጋ ፀታወራው እንደነበር አስታውሳም።
እንደርሱ ከሆነማ እተውሻለሁ ዶክተር” ብሏት ነበር ጉድማን ማዕረጓን ልክ እንደ ስድብ የተጠቀመበት።
የፖሊሶቹ ቤቷ አጠገብ መገኘት ጉድማን ትላንትና ማታ እሷን ለማማለል ሳይሆን ስለ ጥበቃ ያወራው ነገር የእውነቱን መሆኑን እንድትረዳ አደረጋት። ግትርነት የምትወዳቸው የወንዶች ፀባይ ነው መሰለኝ ግትር ወንዶች ደስ ይሏታል። ምንም እንኳን መጨረሻቸው ባልጠበቀችው መልኩ ቢያበቃም ባሏ ዶውግም እንደዚያ ነበር።
አይኗ በእምባ ሲሞላ ኒኪ ተናደደች እና እምባዋን ውጣ፣ መኪናዋንም አቁማ ወደ ቤቷ ገባች። የቤቷን መብራት አብርታ እና ጫማዋን ወርውራ አውልቃ ወደ ማብሰያ ክፍሏ አመራች። አዲስ የገዛችውን ቦርሳዋን ከማብሰያው ክፍል ባልኮኒ ላይ አስቀመጠች። የማታው የዞረ ድምር እስከ አሁን ባይለቃትም ፍሪጂ ውስጥ ያስቀመጠችውን ቨርጅን ሜሪ መጠጥ
ብርጭቆዋን ሞላች። የባልኮኒው ወንበር ላይ ቁጭ እንዳለችም ላፕቶፕዋን
ከፈተች እና ኢ ሜይሏን ተመለከተች፡፡
ምናልባት አኔ ኢ ሜይል ልካ ከሆነ ብላ ነበር ለፕቶፕዋን የከፈተችው።
ከአኔ ግን ምንም የተላከ ኢ ሜይል አላገኘችም።
ሌላ የተላከላት ኢ ሜይል ስለበነረም ከፈተችው። የማታውቀው ኢ ሜይሉን የላከላት ግለሰብ 'ትላንትና ማታ አይቼሻለሁ! በሚል ርዕስ ሥር
ትላንትና ማታ ከጉድማን ጋር አብረው የነበሩበት የዳን ታና ሬስቶራንት ፎቶ
ለጥፏል። ከሆቴሉ ሥር ያለው ሁለተኛው ፎቶ ደግሞ የእሷን ከአንገት በላይ
ያላ ፎቶን ከአንዲት ራቁቷን ከምትወዛወዝ የካርቶን ቪዲዩ ላይ በፎቶ ሾን አያይዞታል። ከፎቶውም በታች “አንቺ ሸርሙጣ እገድልሻለሁ!” የሚል
ማስፈራሪያ ተፅፎበታል።
ኒኪ ይህንን ካየች በኋላ ድንገተኛ ድንጋጤ እና ፍርሃት ወረራት፡፡
በመቀጠልም ድንዝዝ ያለ ስሜት ውስጥ ገብታ ቁጭ አለች።
ስሜቷ ደንዝዞ ብትቀመጥም ጎበዙ አዕምሮዋ የሆነ ነገር ማድረግ እንዳለበት ይወተውታት ጀመረ። ይሄ ቀልድ አይደለም። ይሄ የግድያ ዛቻ ነው፡፡ ለዚያውም የእሷን እያንዳንዱን እንቅስቃሴዎቿን ከሚያውቅ ሰው
ትላንትና ማታ ዳና ሬስቶራንት ውስጥ ከማን ጋር እንደነበረች ሁሉ
ከሚያውቅ ሰው ነው ማስፈራሪያው የተላከላት። ስለዚህ ነገሩን ለፖሊስ
ማሳወቅ ይኖርባታል። አሊያም ደግሞ ለጉድማን ልትነግረው ይገባል።
ግን ደግሞ ትንሽ አመነታች፡ ለመልከመልካሙ መርማሪ ፖሊስ
ጉድማን ነገሩን ማሳወቅ እሱን ይበልጥ ወደ እሷ ህይወት እንዲገባ ማድረግ
አይሆንምን?
ልጠብቅሽ ነው በሚል ሀሳብ ከእሷ ጋር እንዲጣበቅ ምክንያት ማቀበል
አይሆንም?
ግማሽ እሷነቷ ለመርማሪው ነገሩን አሳውቂ ሲላት፣ ግማሽ እና ብልሁ
ሌላኛው እሷነቷ ግን ይህ ትክክል እንዳልሆነ ነገራት።
ጉድማን መልካም ሰው ነው፤ ችግሩን ለመፍታት አስፈላጊውን ጥረት ሁሉ ያደርጋል። ግን ደግሞ ባልደረባው የሰይጣን ቁራጩ ጆንሰን አብሮት
የሚሰራ አጋሩ እስከሆነ ድረስ ሁለቱም የግድ የእሷን ጉዳይ ይመለከቱታል
ማለት ነው። ይሄ የእሱ አጋርነት ደግሞ የሊዛን እና የትሬይን ገዳይ እንዲሁም ደግሞ እሷን ጭምር በመኪና ሊገድላት የሞከረ ሰውን ይዞ ለፍርድ ማቅረብ ያቃተው እንደሆነ እያየችው ነው።
ለማንኛውም ህይወቷ አደጋ ላይ ነው፣ ኒኪ ጥበቃ ያስፈልጋታል።ከጥበቃው በላይ ደግሞ መልስ ትፈልጋለች፡፡ የምትፈልገው መልስ ደግሞ ስለ ግድያዎቹ ብቻ አይደለም። የዶውግን ክህደት ካወቀችበት ጊዜ ጀምሮ
በዋናነት የእሷን ህይወትን መርዞባት እስከ አሁን ድረስ ውስጧን ለሚያደማት
👍2❤1
ጥያቄ መልስ ትፈልጋለች።
የጎግልን መክፈቻ ተጭና ከፈተች። ከዚያም ከመፈለጊያው መስመር
ውስጥ ምዕራብ ሎስ አንጀለስ ውስጥ የሚገኝ የግል መርማሪ የሚል ፅሁፍ
ፃፈች እና ፈልግ የሚለውን ቦታ ተጫነች፣ ሁለተኛው ዕቅዷን ማካሄድ ያለባት አሁን ነው::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።፣፣፣
“እሺ አንድርያ ላጤ ምን ማለት እንደሆነ ታውቂያለሽ?”
አላት ዴሪክ ዊሊያምስ አይ ሆፕ ካፌ ውስጥ ሆኖ አስተናጋጇን እየተመለከታት፡፡
“ዴሪክ አሁን እኮ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ነው።” አለችው ድካም ውስጥ የምትገኘው አስተናጋጅ ኩባያውን በቡና እየሞላችለት፡፡ “ይሄ ከእነዚያ የብልግና ቀልዶችህ አንዱ ከሆነ እኔ ጥሩ ስሜት ውስጥ ስላልሆንኩኝ ልሰማህ አልፈልግም::”
“የብልግና ቀልድ አይደለም። ምናለ አንድ አንዴ እንኳን ዘና ብለሽ ብታወሪኝ አንድሪያ?” አላት ዴሪክ፡፡
አስተናጋጇም ቅንድቧን ቋጥራ “ዴሪክ እስቲ ግድግዳዎቹን በደንብ ተመልከታቸው እና ስታስተናግዱ የአስተናጋጁን ፈገግታን ይጨምራል
የሚል ማሳሰቢያ ተለጥፏል?” ብላ ስትመልስለት ዴሪክ ከት ብሎ ቅርፅ
አልባው ሰውነቱ እስኪንዘፈዘፍ ድረስ ሳቀ፡፡ አንድሪያ የሚፈልጋት አይነት
ሴት ናት። ብቸኛ አስተናጋጅ ሆና በሰዓት ስምንት ዶላር እየተከፈላት የምትሠራ ቀልደኛ ሴት።
“ላጤ ማለት አንድን ስህተት ዳግመኛ የማይሰራ ሰው ነው:: አያስቅም
ውዴ? እመኚኝ፡፡ ሌላ ደግሞ ቀልድ አለኝ” አላት፡፡
አንድሪያም ፈገግ ብላ ሁለት ሜኖዎችን ጠረጴዛ ላይ እያስቀመጠች
ተመለከተችው፡፡
“ፍርድ ቤት ለልጅ ማሳደጊያ ብሎ የሚቆርጠው ገንዘብ ምን ይባላል?”
ብሎ ሲጠይቃት ከአጠገቡ ሄደች፡፡
“ይሄ ደግሞ ተንደላቅቆ በሰው ገንዘብ መኖር ማለት ነው” አላት።
የመጨረሻው ቀልድ ለዴሪክ ዊሊያምስ የራሱን ህይወት የሚገልጽ ነበር፡፡ የቀድሞ ሚስቱ ፍርድ ቤት ገትራው ነበርና። “እኔ የግል መርማሪ ነኝ የተከበሩ ዳኛ” ብሎ የመጨረሻው የፍርድ ቀን ቀርቦ በነበረበት ጊዜ ላይ “እኔ ጠበቃ አይደለሁም ወይንም ደግሞ የኢንቨስትመንት ባንከርም አይደለሁም ወይም ደግሞ ሳንፍራንሲስኮ ውስጥ የምኖር የኮምፒውተር ባለሙያም አይደለሁም፡፡ የኢንተርኔት ካምፓኒውን ፓሎ አልቶ' ብዬ እንኳን መፃፍ የማልችል ሰው ነኝ” ነበር ያለው፡፡
“ይህን በመስማቴ አዝናለሁ።” አለችው ሴቷ ዳኛ፡፡ የሆነች የሴቶች መብት አቀንቃኝ ነገር ናት ግን እስር ቤት እንዴት እንደሚፃፍ እንደምታውቅ እርግጠኛ ነኝ። ስለዚህ ተገቢውን የልጅህን ማሳደጊያ ብርዐለሚስትህ ሶላኔ የማትከፍል ከሆነ እስር ቤት ነው የሚጠብቅህ” ብላ
ሚስ ሶላኔ። ስሟን ደግሞ ከመቼው ቀየረችው? ምን የራሷን ብቻ ፍቺውን ከፈፀመች በኋላ የወንድ ልጃቸው ስም ላይም የራሷን ስም ከትታበት በፍርድ ቤት ስሙን ቀይራለታለች። ሀንተር ሶላኔ ዊሊያምስ ብላዋለች። አሁን ምን ይሉታል ለአንድ የስምንት ዓመት ወንድ ልጅ ይህንን ስም መስጠት? እንዴ ገና ከአሁኑ የሴት ስም ሰጥታው ልጁን ግብረ
ስዶማዊ ልታደርገው ነው? ለማንኛውም ከፍቺያቸው በኋላ ልጁን ሀንተርን
ብዙ ጊዜ አግኝቶት አያውቅም። ይህንን አስመልክታም “ከእሱ ጋር አንድም
ጊዜ ቢሆን አብረኸው አሳልፈህ አታውቅም ዴሪክ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ደግሞ ህጉ ምን እንደሚል ላንተ አልነግርህም!” እያለችም ታስፈራራው ነበር።
“ሚስተር ዊሊያምስ?” የሚል ድንገተኛ ድምፅ ሲሰማ ደንብሮ ተነሳ። እጁ ላይ ይዞት የነበረውን ቡና የለበሰው ሸሚዝ ላይ ተደፋበት፡፡ “ማን…” ብሎ እየተራገመ በቡናው ምክንያት ሰውነቱ ላይ የተጣበቀውን ሸሚዝ ከገላው ላይ እያስለቀቀ ወደ ጎን ሲመለከት አንድሪያ ድምጿን አጥፍታ ስትስቅ ተመለከታት፡
“በእግዚአብሔር ስም! በጣም ይቅርታ” አለችው አጠገቡ የቆመችው ባለ
ቢጫ ፀጉር ቆንጆ ሴት የኔ ጥፋት ነው”
አይደለም አንቺ ምንም ጥፋት የለብሽም” ብሎ በሶፍት ሸሚዙን እየጠረገ “የሆነ ነገርን እያሰብኩኝ ነበር፡፡ የሆነ ቅዥት ነገር። ባልሳሳት ዶክተር ሮበርትስ ነሽ?”
ኒኪ ብለህ ልትጠራኝ ትችላለህ። በጠዋት ልታገኘኝ ስለተስማማህልኝ አመሰግናለሁ፡፡” አለችው እና እጇን ለሰላምታ ዘረጋችለት። ዴሪክ ቀና ብሎ
ሲመለከታት የዞምቢው ግድያ በሚል ርዕስ በቴሌቪዥን ላይ ካያት በላይ
ውብ ናት፡፡ ዶክተር ሮበርትስ እኩለ ለሊት ላይ ነበር የደወለችለት። ስልኩን ካላነሳም የድምፅ መልዕክት ልትተውለት አስባ ነበር የደወለችለት፡፡ ነገር ግን ዊሊያምስ ስልኩን አነሳ እና አወራት። በግሏ ልታውቅ የምትፈልጋቸው ነገሮች ስላሉ የግል መርማሪ እንደምትፈልግና ጠዋት ላይ መገናኘት ይችሉ እንደሆነም ጠየቀችው፡፡ ጠዋት ላይ ሊያገኛት ግድ የሆነበት ምክንያት ገንዘብ ስለሚያስፈልገው ብቻ አይደለም፡፡ የድምጿ ቅላፄ እውነተኛ የተስፋ መቁረጥ ስሜት የሚታይበት መሆኑን ስለተረዳና በዚህ ስሜት ውስጥ
የሚገኙ ደምበኞቹ ያለማንገራገር የተጠየቁትን ገንዘብ ለመክፈል ያላቸውን
ዝግጁነት በማወቁ ጭምር ነው፡፡
✨ይቀጥላል✨
የጎግልን መክፈቻ ተጭና ከፈተች። ከዚያም ከመፈለጊያው መስመር
ውስጥ ምዕራብ ሎስ አንጀለስ ውስጥ የሚገኝ የግል መርማሪ የሚል ፅሁፍ
ፃፈች እና ፈልግ የሚለውን ቦታ ተጫነች፣ ሁለተኛው ዕቅዷን ማካሄድ ያለባት አሁን ነው::
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።፣፣፣
“እሺ አንድርያ ላጤ ምን ማለት እንደሆነ ታውቂያለሽ?”
አላት ዴሪክ ዊሊያምስ አይ ሆፕ ካፌ ውስጥ ሆኖ አስተናጋጇን እየተመለከታት፡፡
“ዴሪክ አሁን እኮ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ነው።” አለችው ድካም ውስጥ የምትገኘው አስተናጋጅ ኩባያውን በቡና እየሞላችለት፡፡ “ይሄ ከእነዚያ የብልግና ቀልዶችህ አንዱ ከሆነ እኔ ጥሩ ስሜት ውስጥ ስላልሆንኩኝ ልሰማህ አልፈልግም::”
“የብልግና ቀልድ አይደለም። ምናለ አንድ አንዴ እንኳን ዘና ብለሽ ብታወሪኝ አንድሪያ?” አላት ዴሪክ፡፡
አስተናጋጇም ቅንድቧን ቋጥራ “ዴሪክ እስቲ ግድግዳዎቹን በደንብ ተመልከታቸው እና ስታስተናግዱ የአስተናጋጁን ፈገግታን ይጨምራል
የሚል ማሳሰቢያ ተለጥፏል?” ብላ ስትመልስለት ዴሪክ ከት ብሎ ቅርፅ
አልባው ሰውነቱ እስኪንዘፈዘፍ ድረስ ሳቀ፡፡ አንድሪያ የሚፈልጋት አይነት
ሴት ናት። ብቸኛ አስተናጋጅ ሆና በሰዓት ስምንት ዶላር እየተከፈላት የምትሠራ ቀልደኛ ሴት።
“ላጤ ማለት አንድን ስህተት ዳግመኛ የማይሰራ ሰው ነው:: አያስቅም
ውዴ? እመኚኝ፡፡ ሌላ ደግሞ ቀልድ አለኝ” አላት፡፡
አንድሪያም ፈገግ ብላ ሁለት ሜኖዎችን ጠረጴዛ ላይ እያስቀመጠች
ተመለከተችው፡፡
“ፍርድ ቤት ለልጅ ማሳደጊያ ብሎ የሚቆርጠው ገንዘብ ምን ይባላል?”
ብሎ ሲጠይቃት ከአጠገቡ ሄደች፡፡
“ይሄ ደግሞ ተንደላቅቆ በሰው ገንዘብ መኖር ማለት ነው” አላት።
የመጨረሻው ቀልድ ለዴሪክ ዊሊያምስ የራሱን ህይወት የሚገልጽ ነበር፡፡ የቀድሞ ሚስቱ ፍርድ ቤት ገትራው ነበርና። “እኔ የግል መርማሪ ነኝ የተከበሩ ዳኛ” ብሎ የመጨረሻው የፍርድ ቀን ቀርቦ በነበረበት ጊዜ ላይ “እኔ ጠበቃ አይደለሁም ወይንም ደግሞ የኢንቨስትመንት ባንከርም አይደለሁም ወይም ደግሞ ሳንፍራንሲስኮ ውስጥ የምኖር የኮምፒውተር ባለሙያም አይደለሁም፡፡ የኢንተርኔት ካምፓኒውን ፓሎ አልቶ' ብዬ እንኳን መፃፍ የማልችል ሰው ነኝ” ነበር ያለው፡፡
“ይህን በመስማቴ አዝናለሁ።” አለችው ሴቷ ዳኛ፡፡ የሆነች የሴቶች መብት አቀንቃኝ ነገር ናት ግን እስር ቤት እንዴት እንደሚፃፍ እንደምታውቅ እርግጠኛ ነኝ። ስለዚህ ተገቢውን የልጅህን ማሳደጊያ ብርዐለሚስትህ ሶላኔ የማትከፍል ከሆነ እስር ቤት ነው የሚጠብቅህ” ብላ
ሚስ ሶላኔ። ስሟን ደግሞ ከመቼው ቀየረችው? ምን የራሷን ብቻ ፍቺውን ከፈፀመች በኋላ የወንድ ልጃቸው ስም ላይም የራሷን ስም ከትታበት በፍርድ ቤት ስሙን ቀይራለታለች። ሀንተር ሶላኔ ዊሊያምስ ብላዋለች። አሁን ምን ይሉታል ለአንድ የስምንት ዓመት ወንድ ልጅ ይህንን ስም መስጠት? እንዴ ገና ከአሁኑ የሴት ስም ሰጥታው ልጁን ግብረ
ስዶማዊ ልታደርገው ነው? ለማንኛውም ከፍቺያቸው በኋላ ልጁን ሀንተርን
ብዙ ጊዜ አግኝቶት አያውቅም። ይህንን አስመልክታም “ከእሱ ጋር አንድም
ጊዜ ቢሆን አብረኸው አሳልፈህ አታውቅም ዴሪክ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ደግሞ ህጉ ምን እንደሚል ላንተ አልነግርህም!” እያለችም ታስፈራራው ነበር።
“ሚስተር ዊሊያምስ?” የሚል ድንገተኛ ድምፅ ሲሰማ ደንብሮ ተነሳ። እጁ ላይ ይዞት የነበረውን ቡና የለበሰው ሸሚዝ ላይ ተደፋበት፡፡ “ማን…” ብሎ እየተራገመ በቡናው ምክንያት ሰውነቱ ላይ የተጣበቀውን ሸሚዝ ከገላው ላይ እያስለቀቀ ወደ ጎን ሲመለከት አንድሪያ ድምጿን አጥፍታ ስትስቅ ተመለከታት፡
“በእግዚአብሔር ስም! በጣም ይቅርታ” አለችው አጠገቡ የቆመችው ባለ
ቢጫ ፀጉር ቆንጆ ሴት የኔ ጥፋት ነው”
አይደለም አንቺ ምንም ጥፋት የለብሽም” ብሎ በሶፍት ሸሚዙን እየጠረገ “የሆነ ነገርን እያሰብኩኝ ነበር፡፡ የሆነ ቅዥት ነገር። ባልሳሳት ዶክተር ሮበርትስ ነሽ?”
ኒኪ ብለህ ልትጠራኝ ትችላለህ። በጠዋት ልታገኘኝ ስለተስማማህልኝ አመሰግናለሁ፡፡” አለችው እና እጇን ለሰላምታ ዘረጋችለት። ዴሪክ ቀና ብሎ
ሲመለከታት የዞምቢው ግድያ በሚል ርዕስ በቴሌቪዥን ላይ ካያት በላይ
ውብ ናት፡፡ ዶክተር ሮበርትስ እኩለ ለሊት ላይ ነበር የደወለችለት። ስልኩን ካላነሳም የድምፅ መልዕክት ልትተውለት አስባ ነበር የደወለችለት፡፡ ነገር ግን ዊሊያምስ ስልኩን አነሳ እና አወራት። በግሏ ልታውቅ የምትፈልጋቸው ነገሮች ስላሉ የግል መርማሪ እንደምትፈልግና ጠዋት ላይ መገናኘት ይችሉ እንደሆነም ጠየቀችው፡፡ ጠዋት ላይ ሊያገኛት ግድ የሆነበት ምክንያት ገንዘብ ስለሚያስፈልገው ብቻ አይደለም፡፡ የድምጿ ቅላፄ እውነተኛ የተስፋ መቁረጥ ስሜት የሚታይበት መሆኑን ስለተረዳና በዚህ ስሜት ውስጥ
የሚገኙ ደምበኞቹ ያለማንገራገር የተጠየቁትን ገንዘብ ለመክፈል ያላቸውን
ዝግጁነት በማወቁ ጭምር ነው፡፡
✨ይቀጥላል✨
👍2❤1🔥1
#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....በጥፊ ጆሮ ግንዷን እናጋው፡፡
ለጥቂት ደቂቃዎች ያለችበት ጠፋት፤ዘሪያዋ ጨለማ ለበሰ፡፡ እዛው
አፓርትመንት ክፍሏ ውስጥ እጆቿንና እግርቿን ከአልጋዋ ጋር በአንሶላ
ጨርቅ ጥፍር አድርገው አስረው እንዳትጮህ አፏ ውስጥ ጨርቅ ጎስጉሰው ለጉመው አጋድመዋታል፡፡
“ንገሪኝ!” አለ ድጋሚ ሊያጣፋት እየተንጠራራ “የት ነው ያለው?
ትነግሪኛለሽ አትነግሪኝም?”
ጭንቅላቷን በጭንቀት አርገፈገፈችው:: ከተለጎመው አፏ ጀርባ ጉሮሮዋ . “የት እንዳለ አላውቅም:: እውነቴን ነው!” አለች:: ድምፅ ግን አላወጣችም፡፡
ውልብ አለባት ድጋሚ፡፡ ጆሮዋ ላይ ሌላ ጥፊ ደወለ፡፡
“ንገሪኝ!”
ዱላው እየጨመረ በመጣ ቁጥር እልኋና ቁጣዋ እንዴት ተደፈርኩ ባያነቷ እንደጨው እየሟመ ለማይታክተው እንባዋ እስረከበዋታል፡፡ ፀጉሯ
ሲጨመደድ ተሰማት::
“ንገሪኝ! የት ነው ያለው?”
ድጋሚ በጥፊ አይኖቿን ከደናቸው፡፡
“ንገሪኝ!”
ተከትሎ ምን እንደተናገረ አልሰማችውም:: ጆሮዋ ላይ የሚደውለውን ስቃይ ተከትሎ ዙሪያዋ ፅልመት ተከናነበ፡፡ አይኖቿን ድጋሚ ስትገልጣቸው ሰውነቷን ክፉኛ ቀዘቀዛት፡፡ለሶስተኛ ጊዜ ውሃ አፍስሰውባታል፡፡
አልጋዋ በየደቂቃው ህሊናዋን በሳተች ቁጥር በሚቸለስባት ቀዝቃዛ ውሃ
ረስርሳል:: የለበሰችው ስስ ቀሚስ እላይዋ ላይ ተጣብቋል፡፡
ዓይኖቿን ግርብብ አድርጋ ተመሰከተቻቸው፡፡ ሶስቱም በአልጋዋ
ዙሪያ ቆመው ቁልቁል ይመለከቷታል፡፡ ሁለቱን አታቃቸውም፡፡ ሶስተኛው
ግን ያው የህዋሷ መሪ ማርቆስ ነበር፡፡ በጠባሳ የተገመሰ ፊቱን ቁልቁል
አንዘርቦ ይመለከታታል፡፡ ደጉን የተወያየችው የገዛ ጓደኛዋ አልመስልሽ
አላት፡፡ አይኖቿን ጭምቅ አድርጋ ጨፈነቻቸው፡፡ በተንጋለለችበት እንባዋ
የገዛ አይኖቿን እንደጨው እየለበለበ ፈሰሰ፡፡
“ከሃዲ!” አለ ሰስተግራዋ የቆመ ሌሊቱን ሲጠፈጥፋት ያደረው ሰው ድንገት ፊቱን መልሶ የመኝታ ክፍሏን በር ከፍቶ እየወጣ፡፡
በክፍሉ ውስጥ የቀሩት ሁለት ሰዎች ለጥቂት ደቂቃዎች ያለ እንቅስቃሴ ቁልቁል ሲመለከቷት ቆዩ፡፡ ወዲያው ማርቆስ ጠጋ ብሎ አፏ የተለጎመበትን ጨርቅ መፍታት ጀመረ፡፡ ሽቅብ ፊቱን ስትመለከተው ከዓመት በላይ የምታውቀው አብራው የቀለደችና የሳቀች ያው የድሮው የህዋሷ መሪ ማርቆስ መሆኑን ማመን አቃታት፡፡
“ምን ማድረግህ ነው?” አለ ከበስተግርጌ የቆመው ጺማም ሰውዬ ማርቆስ አፏ የተለጎመበትን ጨርቅ ሲፈታላት ሲያይ እየተቁነጠነጠ።
ማርቆስ ለሰውየው መልስ ሳይሰጠው አፏን ሞልቶ ተርፎ የነበረውን ቡትቶ ጨርቅ ጎትቶ አወጣላት፡፡ ተበርግዶ የቆየ መንጋጋዋ የራሷ መንጋጋ እንዳልሆነ ሁሉ አልገጥምልሽ አላት፡፡ ደርቆ የቆየ ጉርሮዋ የገዛ ምራቋን አልውጥልሽ አላት፡፡ እንባዋ ብቻ ጉንጮቿን እየተለተለ መውረዱን
ቀጠለ፡፡
“ርብቃ …ለምን ለእኛም ለራስሽም አስቸጋሪ ትሆኛለሽ?” ማርቆስ
ቁልቁል እየተመላከተ ተማፀናት፡፡ “ርብቃ ልለምንሽ የት እንዳለ ንገሪንና
ይህ ሁሉ ያብቃ፡፡” ተለማመጣት፡፡
ለምን አይገባቸውም?! ናትናኤል የት እንደለ ኣላውቅም ስትላቸው ለምን አያምኗትም?! እንዴት አድርጋ ነው እውነቱን እውነት ነው የምትላቸው?
“የት እንዳለ አላውቅም፡፡” ልትል ፈለገችና ጉሮዋ አልታዘዝሽ አላት፡፡ በጀርባዋ በተንጋለለችበት ጭንቅላቷን ነቀነቀች፡፡
“ርብቃ ጊዜ በወሰድሽ ቁጥር ሁኔታው ለራስሽ እየከፋ ነው የሚሄደው፡፡ የምትጋፈጫቸው ሰዎች ትዕግሥታቸው ያለቀና ቁጣቸው ወደ ዕልህ የተቀየረ ራሳቸውን መቆጣጠር የማይችሉ ናቸው:: ርብቃ እነዚህ ሰዎች ሊያደርጉት የሚገፋፉትን ደግሞ ማንም አይወደውም፡፡ አንቺ ሴት ነሽ፡፡ እነዚህን ሰዎች የሚቋቋም የመንፈስ ጠንካራነት የለሽም:: በቀላሉ እንደቀርከሃ ሊሰባብሩሽ ይችላሉ፡፡ በቀላሉ! እባክሽን ንገሪኝ፡፡፡ ናትናኤል የት ነው?” የሌሊት ሁኔታዋን መቋቋም አቅቶት ሲቁነጠነጥ ያደረው
ማርቆስ የባሰ ከመምጣቱ በፊት ሊያሳምናት ታገለ፡፡
አ....አላውቅም፡፡” አለችው እንባዋን እያስተናገደች::
“ጥሩ፡፡ መስሪያ ቤትሽ ደውሉ ሲያጣሽና ስራ ከገባሽ ውሰሽ ማደርሽን ሲረዳ እንዴት እዚህ አልደወለም?”
“ፈርቶ ይሆናል... እኔ ምን አውቃለሁ፡፡” እውነተኛነቷን ይገልፅላት ይመስል ድምጿን አለሰለሰችው::
“ምን? ማንን ነው የሚፈራው?”
“እናንተን፡፡” አለች በለቅሶ መሃል፡፡
“አየሽ ይህ ማለት አንቺ ከእኛ ጋር ግንኙነት እንዳለሽ አውቋል ወይም በፊትም ያውቅ ነበር ማለት ነው፡፡ ይህን ሊያውቅ የሚችለው ደግሞ አንቺ....”
አልነገርኩትም!” አለች አቅጣጫውን ስትረዳ አቋርጣው፡፡ “እኔ አልነገርኩትም፡፡እኔ በእርሱ ላይ መረጃ ስስበስብ መቆየቴንም ጭራሽ አያውቅም፡፡ ግን እዚህ ሲመጣ ልታገኙት እንደምትችሉ ጠርጥሮ ይሆናል፡፡”
ለምን ድጋሚ መሥሪያ ቤትሽ ስልክ አልደወለም? ባለፈው ጊዜ ሲደውል ጓደኛሽ ቢሮ ከገባሽ ዉስሽ ማደርሽን እንድትነግረው አድርገናል፡፡እዚህ መደወል ወይ መምጣት ነበረበት፡፡ አልመጣም፧ አልደወለም:: መሥሪያ
ቤትሽም መልሶ አልደወለም:: ለምን?”
“አላውቅም::” እለች በማስተዛዘን፡፡
“ውሽት አውቋል… ሁሉንም ተረድቶታል:: ለዚህ ነው ሊገናኝሽ ያልሞከረ፡፡ ባያውቅ ኖር..”
“ውሸቴን አይደለም!” አቋረጠችው “እመኑኝ ናትናኤል ምንም የሚያውቀው ነገር የለም ናት…”
“ያውቃል! ያውቃል! ምንም የማያውቅ ሰው በጭካኔ የሁለት ሰው ነፍስ አጥፍቶ አይሰወርም፡፡ ትሰሚኛለሽ? የፈጸመው ወንጀል ምንም የማያውቅ ሰው የሚፈጽመው አይደለም!” ትከሻዋን በሁለት እጆቹ ይዞ ነቅነቃት፡፡
“ናትናኤል ሰው ፡ አይገድልም...ውሸት
ነው፡፡” ለራሷ ፡ ነበር የተናገረችው፡፡
“ርብቃ…. ሰዎቻችን ያውቁታል፡፡ ለይተው ስላወቁትም ነው የተከታሉት፡፡ ይገባሻል? የካልቨርትን አድራሻ ከሴትየዋ ማግኘት ስላልቻለ ምናልባትም አድራሻውን አስገድዶ ካውጣጣት በኋላ ነው ደረቷን በጥይት የበሳው፤ ገድሏት የሄደው፡፡
አስታውሽ እሷን ብቻ አይደለም ያጠፋው!
የኛንም ሰው ነው:: ርብቃ… እባብ ነው ሰውዬሽ፡፡ ሁላችንንም አታሎናል፡፡
ምንም የማያውቅ የዋህ መስሎ አታሎናል፡፡ አንቺንም አታሎሻል፡፡ አብረን
ልናቆመው ይገባናል፡፡ ንገሪኝ፤ የት ነው የተሸሸገው?”
“አላውቀውም አልኩህ፡፡”
ገፁ በንዴት ተኮማተረ፡፡
“ርብቃ” አይኖቹን አጥብቦ ተመለከታት፡፡ “በአንድ ወቅት ከጎናችን መቆምሽን አንዘነጋውም፤ ያ የሩቅ ትዝታ አይደለም፤ ግን ደግሞ መረባችን በከዳተኞች ምላጭ ሲበጣጠስና ውጥናችን በባንዳዎች ራስ ወዳድነት እርቃኑን ወጥቶ እያንዳንዳችን ለስደትና ለሞት ስንዳረግ በዝምታ መመልከት አንችልም፡፡ ይህ እንዳይሆን ደግሞ የምንጠላውንም ነገር ቢሆን ለማድረግ እንገደዳለን፡፡ ርብቃ ትሰሚኛለሽ? መንፈስሽ መኮሳሽት ካለበት እናኮላሽዋለን፤ሰውነትሽ መዋረድ ካለበት እናዋርደዋለን! ህሊናሽ መጨቅየት ካለበት እናጨቅየዋለን… የማታ ማታ የጠየቅንሽን ሁሉ ታወጪዋለሽ፡፡ ይህ ከመሆኑ በፊት አስተውይ፡፡ ናትናኤል አታሎሻል! የስጋ ፍላጎትሽን ተጠቅሞ
ምስጢራችንን ከቀዳ በኋላ አጋልጦሽ ተሰውሯል፡፡ የት ነው ያለው?
ናትናኤል የት ነው?”
“አላውቅም'ኮ” እንባዋ ገና ድሮ በቀደደው ቦይ ያንቆረቆር ጀመር፡፡
የመኝታ ቤቷ በር ተከፍቶ ሦስት ሰዎች ተከታትለው ገቡ፡፡ ሁለቱን አይታቸው አታወቅም አንደኛው ግን ከትላንት ጀምሮ ሲቀጠቅጣት የቆየ ነው ከፊት ቀደም ያለው ሰው በእድሜ ጠና ያለ ይመስላል፡፡ ወደፊት ራመድ ብሎ ወደ አልጋዋ ግርጌ ከተጠጋ በኋላ በክፍሉ ውስጥ ለተሰበሰቡት ሰዎች እንዲፈቷት ምልክት ሰጣቸውና ከማርቆስ ጋር በሹክሹክታ ይነጋገር ጀመር
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....በጥፊ ጆሮ ግንዷን እናጋው፡፡
ለጥቂት ደቂቃዎች ያለችበት ጠፋት፤ዘሪያዋ ጨለማ ለበሰ፡፡ እዛው
አፓርትመንት ክፍሏ ውስጥ እጆቿንና እግርቿን ከአልጋዋ ጋር በአንሶላ
ጨርቅ ጥፍር አድርገው አስረው እንዳትጮህ አፏ ውስጥ ጨርቅ ጎስጉሰው ለጉመው አጋድመዋታል፡፡
“ንገሪኝ!” አለ ድጋሚ ሊያጣፋት እየተንጠራራ “የት ነው ያለው?
ትነግሪኛለሽ አትነግሪኝም?”
ጭንቅላቷን በጭንቀት አርገፈገፈችው:: ከተለጎመው አፏ ጀርባ ጉሮሮዋ . “የት እንዳለ አላውቅም:: እውነቴን ነው!” አለች:: ድምፅ ግን አላወጣችም፡፡
ውልብ አለባት ድጋሚ፡፡ ጆሮዋ ላይ ሌላ ጥፊ ደወለ፡፡
“ንገሪኝ!”
ዱላው እየጨመረ በመጣ ቁጥር እልኋና ቁጣዋ እንዴት ተደፈርኩ ባያነቷ እንደጨው እየሟመ ለማይታክተው እንባዋ እስረከበዋታል፡፡ ፀጉሯ
ሲጨመደድ ተሰማት::
“ንገሪኝ! የት ነው ያለው?”
ድጋሚ በጥፊ አይኖቿን ከደናቸው፡፡
“ንገሪኝ!”
ተከትሎ ምን እንደተናገረ አልሰማችውም:: ጆሮዋ ላይ የሚደውለውን ስቃይ ተከትሎ ዙሪያዋ ፅልመት ተከናነበ፡፡ አይኖቿን ድጋሚ ስትገልጣቸው ሰውነቷን ክፉኛ ቀዘቀዛት፡፡ለሶስተኛ ጊዜ ውሃ አፍስሰውባታል፡፡
አልጋዋ በየደቂቃው ህሊናዋን በሳተች ቁጥር በሚቸለስባት ቀዝቃዛ ውሃ
ረስርሳል:: የለበሰችው ስስ ቀሚስ እላይዋ ላይ ተጣብቋል፡፡
ዓይኖቿን ግርብብ አድርጋ ተመሰከተቻቸው፡፡ ሶስቱም በአልጋዋ
ዙሪያ ቆመው ቁልቁል ይመለከቷታል፡፡ ሁለቱን አታቃቸውም፡፡ ሶስተኛው
ግን ያው የህዋሷ መሪ ማርቆስ ነበር፡፡ በጠባሳ የተገመሰ ፊቱን ቁልቁል
አንዘርቦ ይመለከታታል፡፡ ደጉን የተወያየችው የገዛ ጓደኛዋ አልመስልሽ
አላት፡፡ አይኖቿን ጭምቅ አድርጋ ጨፈነቻቸው፡፡ በተንጋለለችበት እንባዋ
የገዛ አይኖቿን እንደጨው እየለበለበ ፈሰሰ፡፡
“ከሃዲ!” አለ ሰስተግራዋ የቆመ ሌሊቱን ሲጠፈጥፋት ያደረው ሰው ድንገት ፊቱን መልሶ የመኝታ ክፍሏን በር ከፍቶ እየወጣ፡፡
በክፍሉ ውስጥ የቀሩት ሁለት ሰዎች ለጥቂት ደቂቃዎች ያለ እንቅስቃሴ ቁልቁል ሲመለከቷት ቆዩ፡፡ ወዲያው ማርቆስ ጠጋ ብሎ አፏ የተለጎመበትን ጨርቅ መፍታት ጀመረ፡፡ ሽቅብ ፊቱን ስትመለከተው ከዓመት በላይ የምታውቀው አብራው የቀለደችና የሳቀች ያው የድሮው የህዋሷ መሪ ማርቆስ መሆኑን ማመን አቃታት፡፡
“ምን ማድረግህ ነው?” አለ ከበስተግርጌ የቆመው ጺማም ሰውዬ ማርቆስ አፏ የተለጎመበትን ጨርቅ ሲፈታላት ሲያይ እየተቁነጠነጠ።
ማርቆስ ለሰውየው መልስ ሳይሰጠው አፏን ሞልቶ ተርፎ የነበረውን ቡትቶ ጨርቅ ጎትቶ አወጣላት፡፡ ተበርግዶ የቆየ መንጋጋዋ የራሷ መንጋጋ እንዳልሆነ ሁሉ አልገጥምልሽ አላት፡፡ ደርቆ የቆየ ጉርሮዋ የገዛ ምራቋን አልውጥልሽ አላት፡፡ እንባዋ ብቻ ጉንጮቿን እየተለተለ መውረዱን
ቀጠለ፡፡
“ርብቃ …ለምን ለእኛም ለራስሽም አስቸጋሪ ትሆኛለሽ?” ማርቆስ
ቁልቁል እየተመላከተ ተማፀናት፡፡ “ርብቃ ልለምንሽ የት እንዳለ ንገሪንና
ይህ ሁሉ ያብቃ፡፡” ተለማመጣት፡፡
ለምን አይገባቸውም?! ናትናኤል የት እንደለ ኣላውቅም ስትላቸው ለምን አያምኗትም?! እንዴት አድርጋ ነው እውነቱን እውነት ነው የምትላቸው?
“የት እንዳለ አላውቅም፡፡” ልትል ፈለገችና ጉሮዋ አልታዘዝሽ አላት፡፡ በጀርባዋ በተንጋለለችበት ጭንቅላቷን ነቀነቀች፡፡
“ርብቃ ጊዜ በወሰድሽ ቁጥር ሁኔታው ለራስሽ እየከፋ ነው የሚሄደው፡፡ የምትጋፈጫቸው ሰዎች ትዕግሥታቸው ያለቀና ቁጣቸው ወደ ዕልህ የተቀየረ ራሳቸውን መቆጣጠር የማይችሉ ናቸው:: ርብቃ እነዚህ ሰዎች ሊያደርጉት የሚገፋፉትን ደግሞ ማንም አይወደውም፡፡ አንቺ ሴት ነሽ፡፡ እነዚህን ሰዎች የሚቋቋም የመንፈስ ጠንካራነት የለሽም:: በቀላሉ እንደቀርከሃ ሊሰባብሩሽ ይችላሉ፡፡ በቀላሉ! እባክሽን ንገሪኝ፡፡፡ ናትናኤል የት ነው?” የሌሊት ሁኔታዋን መቋቋም አቅቶት ሲቁነጠነጥ ያደረው
ማርቆስ የባሰ ከመምጣቱ በፊት ሊያሳምናት ታገለ፡፡
አ....አላውቅም፡፡” አለችው እንባዋን እያስተናገደች::
“ጥሩ፡፡ መስሪያ ቤትሽ ደውሉ ሲያጣሽና ስራ ከገባሽ ውሰሽ ማደርሽን ሲረዳ እንዴት እዚህ አልደወለም?”
“ፈርቶ ይሆናል... እኔ ምን አውቃለሁ፡፡” እውነተኛነቷን ይገልፅላት ይመስል ድምጿን አለሰለሰችው::
“ምን? ማንን ነው የሚፈራው?”
“እናንተን፡፡” አለች በለቅሶ መሃል፡፡
“አየሽ ይህ ማለት አንቺ ከእኛ ጋር ግንኙነት እንዳለሽ አውቋል ወይም በፊትም ያውቅ ነበር ማለት ነው፡፡ ይህን ሊያውቅ የሚችለው ደግሞ አንቺ....”
አልነገርኩትም!” አለች አቅጣጫውን ስትረዳ አቋርጣው፡፡ “እኔ አልነገርኩትም፡፡እኔ በእርሱ ላይ መረጃ ስስበስብ መቆየቴንም ጭራሽ አያውቅም፡፡ ግን እዚህ ሲመጣ ልታገኙት እንደምትችሉ ጠርጥሮ ይሆናል፡፡”
ለምን ድጋሚ መሥሪያ ቤትሽ ስልክ አልደወለም? ባለፈው ጊዜ ሲደውል ጓደኛሽ ቢሮ ከገባሽ ዉስሽ ማደርሽን እንድትነግረው አድርገናል፡፡እዚህ መደወል ወይ መምጣት ነበረበት፡፡ አልመጣም፧ አልደወለም:: መሥሪያ
ቤትሽም መልሶ አልደወለም:: ለምን?”
“አላውቅም::” እለች በማስተዛዘን፡፡
“ውሽት አውቋል… ሁሉንም ተረድቶታል:: ለዚህ ነው ሊገናኝሽ ያልሞከረ፡፡ ባያውቅ ኖር..”
“ውሸቴን አይደለም!” አቋረጠችው “እመኑኝ ናትናኤል ምንም የሚያውቀው ነገር የለም ናት…”
“ያውቃል! ያውቃል! ምንም የማያውቅ ሰው በጭካኔ የሁለት ሰው ነፍስ አጥፍቶ አይሰወርም፡፡ ትሰሚኛለሽ? የፈጸመው ወንጀል ምንም የማያውቅ ሰው የሚፈጽመው አይደለም!” ትከሻዋን በሁለት እጆቹ ይዞ ነቅነቃት፡፡
“ናትናኤል ሰው ፡ አይገድልም...ውሸት
ነው፡፡” ለራሷ ፡ ነበር የተናገረችው፡፡
“ርብቃ…. ሰዎቻችን ያውቁታል፡፡ ለይተው ስላወቁትም ነው የተከታሉት፡፡ ይገባሻል? የካልቨርትን አድራሻ ከሴትየዋ ማግኘት ስላልቻለ ምናልባትም አድራሻውን አስገድዶ ካውጣጣት በኋላ ነው ደረቷን በጥይት የበሳው፤ ገድሏት የሄደው፡፡
አስታውሽ እሷን ብቻ አይደለም ያጠፋው!
የኛንም ሰው ነው:: ርብቃ… እባብ ነው ሰውዬሽ፡፡ ሁላችንንም አታሎናል፡፡
ምንም የማያውቅ የዋህ መስሎ አታሎናል፡፡ አንቺንም አታሎሻል፡፡ አብረን
ልናቆመው ይገባናል፡፡ ንገሪኝ፤ የት ነው የተሸሸገው?”
“አላውቀውም አልኩህ፡፡”
ገፁ በንዴት ተኮማተረ፡፡
“ርብቃ” አይኖቹን አጥብቦ ተመለከታት፡፡ “በአንድ ወቅት ከጎናችን መቆምሽን አንዘነጋውም፤ ያ የሩቅ ትዝታ አይደለም፤ ግን ደግሞ መረባችን በከዳተኞች ምላጭ ሲበጣጠስና ውጥናችን በባንዳዎች ራስ ወዳድነት እርቃኑን ወጥቶ እያንዳንዳችን ለስደትና ለሞት ስንዳረግ በዝምታ መመልከት አንችልም፡፡ ይህ እንዳይሆን ደግሞ የምንጠላውንም ነገር ቢሆን ለማድረግ እንገደዳለን፡፡ ርብቃ ትሰሚኛለሽ? መንፈስሽ መኮሳሽት ካለበት እናኮላሽዋለን፤ሰውነትሽ መዋረድ ካለበት እናዋርደዋለን! ህሊናሽ መጨቅየት ካለበት እናጨቅየዋለን… የማታ ማታ የጠየቅንሽን ሁሉ ታወጪዋለሽ፡፡ ይህ ከመሆኑ በፊት አስተውይ፡፡ ናትናኤል አታሎሻል! የስጋ ፍላጎትሽን ተጠቅሞ
ምስጢራችንን ከቀዳ በኋላ አጋልጦሽ ተሰውሯል፡፡ የት ነው ያለው?
ናትናኤል የት ነው?”
“አላውቅም'ኮ” እንባዋ ገና ድሮ በቀደደው ቦይ ያንቆረቆር ጀመር፡፡
የመኝታ ቤቷ በር ተከፍቶ ሦስት ሰዎች ተከታትለው ገቡ፡፡ ሁለቱን አይታቸው አታወቅም አንደኛው ግን ከትላንት ጀምሮ ሲቀጠቅጣት የቆየ ነው ከፊት ቀደም ያለው ሰው በእድሜ ጠና ያለ ይመስላል፡፡ ወደፊት ራመድ ብሎ ወደ አልጋዋ ግርጌ ከተጠጋ በኋላ በክፍሉ ውስጥ ለተሰበሰቡት ሰዎች እንዲፈቷት ምልክት ሰጣቸውና ከማርቆስ ጋር በሹክሹክታ ይነጋገር ጀመር
❤1👍1
ተከትለውት የገቡት ሰዎች ፈጠን ብለው እጆቿንና እግሮቿን ፈተው ለሁለት ብብትና ብብቷ ውስጥ ገብተው ከአልጋው ላይ አነሷትና ጥግ ወዳለ ወንበር ተሸክመው ወሰዷት፡፡ እግሮቿ በገዛ ክብደቷ ስር እንደ
ሰንበሌጥ ተልፈሰፈሱባት:: ወንበሩ ላይ ካስቀመጧት በኋላ ከአልጋዋ ግርጌ
የቆመው ሰው ወንበር ስቦ ከፊት ለፊቷ ተቀመጠ፡፡ ዕድሜው ገፋ ያለ
መሆኑን ከጆሮ ግንዶቹና ሪሁ ላይ ጣልጣል ያደረገበት ሽበት ያሳጣል፡፡
የለበሰው ሙሉ ልብስ፣ ያጠለቀው ጫማና የጸመ አከረካክም... የጠገበ ነጋዴ አስመስሎታል፡፡
በውሃ የበሰበሰውን ልብሷን ሲመለክት አይኖቹን ከላይዋ ላይ ሳያነሳ
“ልብስ ደርቡላት::” አለ፡፡ቀልጠፍ ባለ ሁኔታ ከቁም ሳጥኗ ውስጥ
አውጥተው በጋቢ ጠቀለሏት፡፡
“በዚህ ኣይነት ሁኔታ መገናኘታችን በእውነት ያሳዝነኛል፡፡” በተቀመጠበት ወደፊት ዘመም ብሎ ተናገራት፡፡“ድርሻሽን በሚያኮራ ሁኔታ ስትወጪ ቆይተሻል፡፡ እያንዳንዳችን በተለያዩ ምክንያቶች ለስሀተት እንዳረጋለን፡፡ ይህ
ቢያሳዝንም ሊያስቆጣን አይገባም ወደፊት ጎንበስ ብሎ ጉልበቶቿን
እየተመተመ አበረታታት፡ “የሥራ ድርሻዬን መናገሬ ከደንቡ ውጪ ቢሆንም
ሁኔታው የሚጠይቅው በመሆኑ አልደብቅሽም፡፡ በንቅናቄው ውስጥ የመረጃ ክፍል በምሥራቅ አፍሪካ የምድብ ለ መሪ ነኝ፡፡ ብርጋድየር ጀኔራል አብይ ሰናይ እባላለሁ::ምን አይነት አስጊ ሁኔታ ላይ እንዳለን ላስረዳሽ አልሞክርም፡፡ ምክንያቱም በሚገባ ትረጅዋለሽ፡፡ ስለሁኔታው ገለፃ እንደተደረገልሽ ተነግሮኛል፡፡ አልደግመውም፡፡ እንድትረጂኝ ነው የምጠይቅሽ…ቆይ ቆይ” አለ ሰውየው ርብቃ ልታቋርጠው ስትል ቀኝ እጁን ወደፊት ዘርግቶ፡፡ “አስጨርሽኝ፡፡ እንደተነገረሽ ናትናኤል የካልቨርትን ወዳጅ ገድሏታል፡፡
ስለካልቨርት ማንነት በቂ እውቀት እንዳለሽም ነግረውኛል፡፡ ስለዚህ ካልቨርት ስለወዳጁ መገደል ፍንጭ ከደረሰው እርሱ ራሱ እንደዛተው ምሥጢራችንን በቀጥታ በውጪ የስለላ ድርጅቶች አሰበለዚያም ለጋዜጠኞች ነው አሳልፎ የሚሰጠው:: ይህ ምን እንደሚያስከትል ከእኔ እኩል ትረጅዋለሽ፡፡ እርግጥ የሴትየዋን እሬሳ ለጊዜው ሰውረነዋል፡፡በቤቷም ውስጥ ያሉ ሴቶች
ስለሁኔታው እንዳይረዱና እንዳያወሩ የሚቻለው ሁሉ እየተደረገ ነው፡፡ ነገር
ግን አሁንም አንድ እጃችን ያልገባ ውል አለ፡፡ናትናኤል የሴትየዋ ግድያ
በእኛ እንደተፈጸመ አድርጎ ለካልቨርት ሊያስተላልፍ ከቻለ ወይንም የካልቨ
ርትን አድራሻ ደርሶበት ከተገናኘውና ምሥጢሩን ከተረዳ ውጤቱ ለሁላ
ችንም ጥፋት ነው:: እመኝኝ በአሁኗ ሰዓት ናትናኤል ከካልቨርት የበለጠ አደገኛ ነው፤ ሊያጠፋን ይችላል፡፡ እጅግ አደገኛ ሰው ነው፡፡”
“እኔኮ…” አለች ርብቃ እንባዋ በዓኗኗ ሲሞላ ልትውጠው እየታገለች።
“ይገባኛል... ይገባኛል ስሁኔታሽ ተነግሮኛል፡፡” አለ ሰውየው ለአንድ አፍታ ዓይኖቹን ወደ ሆዷ ዝቅ አድርጎ፡፡ «እርግጥ ስህተት ቢሆንም አንዴ ተፈጽሟል። ያረገዝሽው ልጅ የእርሱ ነው፡፡ ለዚህም ነው ሕይወቱን ለአደጋ አሳልፈሽ መስጠቱ የከቀደሽ፤ ይገባኛል፡፡ ወደእዚህ የመጣሁት መሃል ላይ የምንስማማበትን መስመር ለመፍጠር ነው፡፡ አንቺ የት እንዳለ ትነግሪኛለሽ፡፡ አለበለዚያም አጥምጄ እንድይዘው ትረጂኛለሽ፡፡ እኔ ደግሞ በሕይወቱም ላይ ሆነ በአካል ማንኛውም ዓይነት አደጋ እንደማይደርስበት ቃል እገባልሻሁ፡፡ እጃችን እንደገባ እዚህ እናመጣዋለን ወይም አንቺን እርሱን ወደምናቆይበት ስፍራ ፡ እንወስድሻለን፡፡ ለጊዜው ብቻ በቁጥጥር ስር እናቆየዋለን፡፡ ዕቅዳችንን ከውጤት ልናደርስ የቀረን አጭር ጊዜ ነው፡፡ከስድስት ቀን በኋላ አደገኛነቱ ያከትማል፡፡ ሁለታችሁም ነፃ ናችሁ፤ ቃል
እገባልሻለሁ:: ትስማሚያለሽ?” ጎንበስ ብሎ ጉልበቷን በወዳጅነት ስሜት ያዝ!
አደረገው፡፡
“የት እንደተደበቀ አላውቅም...
የት ብዬ ልናገር? "
“ግድ የለም ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ዘጠኝ ሰዓት ላይ መሥሪያ ቤትሽ ጓደኛሽጋ ደውሎ ነበር:: ስላንቺ ማሰቡንም ነግሯታል፡፡ ትንሽ መታመምሽንና ቤትሽ ስልክ ደውሎ ቢያነጋግርሽ እንደሚሻል እንድትነግረው አድርገናል፡፡ በማንኛውም ሰዓት እዚህ ሊደወል ይችላል፡፡ በሚደውልበት ሰዓት በጠና መታመምሽንና እንዲያይሽ መፈለግሽን እስተዛዝነሽ ትነግሪዋለሽ፡፡ በተቻለ መጠን ወጥመዳችን ውስጥ እንዲገባ ታባብያዋለሽ፡፡” ክንዷን ያዝ አድርጎ ተናገሪ- ::
ርብቃ በረጅሙ ተነፈሰች፡፡ ጭንቅላቷ እርስ በእርሱ ይጨቃጨቅ ይከራከር ጀመር... ይገድሉታል እውነት ከሆነ «ሰው ገደለ» ያሉት እውነት ከሆነ አይተውትም.. ሲያታልሏት ነው ሊያግባቧት ነው መስማማት የለባትም…እምቢ ብትል የሚከተላትን ስታስብ አይኖቿ በእንባ ተዘፈቁ፡፡ ያስቃይዋታል.ይደበድቧታል… ያንገላቷታል...
“ጊዜ የለንም... በማንኛውም ደቂቃ ሊደውል ይችላል፡፡ እመኚኝ እጄ እንዲገባ እርጅኝ፣ ቃሌን እጠብቃለሁ፡፡”
“አልችልም::” አለችው እንባዋ በጉንጮቿ እየወረደ፡፡
“ቃሌን ማንም ሊሽረው አይችልም! እመኚኝ፡፡ የምነግርሽ እውነት ነው፡፡ አንዲት ፀጉሩ ከላዩ እትወድቅም፡፡”
“አላምንም ሁላችሁንም ኣላምንም፡፡ ጓደኛውን ገድላችሁታል፡፡ አይደለም? እሱንም አትተውትም፡፡” ድምጿ በጭንቅ ቃተተ፡፡
ከቃሌ በላይ ልሰጥሽ የምችለው ማስተማመኛ የለኝም..ቃሌ ደግሞ
እውነት ነው::”
“አላምንም! ውሸት ነው! ውሽት ነው! ውሸት ነወ፡!…” እንዳትሸነፍ፡
የፈራች ይመስል አይኖቿን ጨፍና ጭንቅላቷን ቀኝና ግራ አላጋችው::
“ስለምንሽ ካልረዳሽኝ አስገድጄሽ የምፈልገውን : እንድትፈጽሚ
ማድረግ እችላለሁ።” ለመጀመሪያ ጊዜ ድምፁ ውስጥ የነበረ ልስላሴ
ሲቆረፍድ ተሰማት፡፡
“አልችልም! ልትገድሉኝ ትችላላችሁ፡፡አይኔ እያየ ለሞቱ አልጠራውም... ግደለኝ!” ሰውነቷን ነዘራት::
“አልገድልሽም፡፡ ያ ፍጹም ስህተት ነው አለ ሰውየው ከተቀመጠበት በእርጋታ እየተነሳ፡፡
ከጀርባው ለቆሙት ሰዎች ምልክት ከሰጣቸው በኋላ ሰእርጋታ ወደ
መስኮቱ ተጠግቶ ውጭ ወጪውን ይመለከት ጀመር፡፡ ከወንበሯ ላይ
ለሁለት ተሸክመው አንስተው ኣልጋዋ ላይ አጋደሟት፡፡ በፍጥነት አፏን ፈልቅቀው ቡትቶ ጨርቅ ጠቅጥቀው ለጎሟት፡፡ኣንዴ ብቻ “ማርቆስ!” አለች በጭንቀት…ያ የምታውቀው የሚያውቃት የህዋሷ መሪ ያግዝላት፣ ያድናት ይመስል፡፡ ከቆመበት አልተነቃነቃም::በጭንቅ የሚውጠው
ማንቁርቱን እላይ እታች ሲያመላልሰው የተጨነቀላት፣ ያዘነላት መሰላት፡፡
ተስፋ አደረገች፡፡ ትክ ብሎ ሲመለከታት ኣይኖቹ እንባ ያቆረዘዙ፡ መሰላት::
ተስፋ አደረገች፡፡ ማርቆስ ግን ከአልጋዋ በስተቀኝ ፈንጠር ብሎ እንደቆመ
ቀረ፡፡ አፏ ሲለጎም ልሳኗ ሲከዳት በአይኖችዋ ተማፀነች::: ዓይኖቹን
ከአይኖቿ ነቅሎ ትንፋሹን እላይ እታች እያመላለሰ ቆሞ ቀረ፡፡ ተስፋ ቆረጠች:: ለማይቀረው ዱላና ስቃይ ተዘጋጅታ ተጋደመች፡፡ ተጠባበቀች….
ኣልጋዎ ላይ ያጋደሟት ሰዎች እጆቿኝ ግራና ቀኝ ከአልጋው ጠርዝ ጋር
ጠፍረው ካሰሯት በኋላ የለበሰችውን ውሃ የበሰበሰ ስስ ቀሚስ ክላይዋ ላይ
እንደ ወረቀት እየቀዳደዱ ያነሱት ጀመር፡፡ ድንገት ሴትነቷ ገንፍሏት ወጣ፡፡
እግሮቿን እያፈራገጠች ወገቧን እየሰበቀች ቀሚሷን እላይዋ ላይ ለማስቀረት
ታገለች… ቀሚሷን ግን ኣላተረፈችውም፡፡ እግሮቿን ግራና ቀኝ በርግደው
ከአልጋው ጠርዞች ጋር ጠፈሯቸው...
የተሰማትን ህፍረት፣ የተሰማትን ውርደት ያጥብላት ይመስል እንባዋ ያለማቋረጥ በዓይኗ ጎንና ጎን ተዥጎደጎደ፡፡ ሃሞቷ ሆዷ ውስጥ የፈሰሰ ይመስል ሰውነቷ በመራራ ተሞላ፡፡ግራና ቀኝ ተበርግደው የታሰሩ
እግሮቿን ከታሰሩበት ገመድ ጋር እያፋተገች ሰውነቷን፣ ሴትነቷን፣
ለመሽፈን፣ ለመደበቅ፣
ሰንበሌጥ ተልፈሰፈሱባት:: ወንበሩ ላይ ካስቀመጧት በኋላ ከአልጋዋ ግርጌ
የቆመው ሰው ወንበር ስቦ ከፊት ለፊቷ ተቀመጠ፡፡ ዕድሜው ገፋ ያለ
መሆኑን ከጆሮ ግንዶቹና ሪሁ ላይ ጣልጣል ያደረገበት ሽበት ያሳጣል፡፡
የለበሰው ሙሉ ልብስ፣ ያጠለቀው ጫማና የጸመ አከረካክም... የጠገበ ነጋዴ አስመስሎታል፡፡
በውሃ የበሰበሰውን ልብሷን ሲመለክት አይኖቹን ከላይዋ ላይ ሳያነሳ
“ልብስ ደርቡላት::” አለ፡፡ቀልጠፍ ባለ ሁኔታ ከቁም ሳጥኗ ውስጥ
አውጥተው በጋቢ ጠቀለሏት፡፡
“በዚህ ኣይነት ሁኔታ መገናኘታችን በእውነት ያሳዝነኛል፡፡” በተቀመጠበት ወደፊት ዘመም ብሎ ተናገራት፡፡“ድርሻሽን በሚያኮራ ሁኔታ ስትወጪ ቆይተሻል፡፡ እያንዳንዳችን በተለያዩ ምክንያቶች ለስሀተት እንዳረጋለን፡፡ ይህ
ቢያሳዝንም ሊያስቆጣን አይገባም ወደፊት ጎንበስ ብሎ ጉልበቶቿን
እየተመተመ አበረታታት፡ “የሥራ ድርሻዬን መናገሬ ከደንቡ ውጪ ቢሆንም
ሁኔታው የሚጠይቅው በመሆኑ አልደብቅሽም፡፡ በንቅናቄው ውስጥ የመረጃ ክፍል በምሥራቅ አፍሪካ የምድብ ለ መሪ ነኝ፡፡ ብርጋድየር ጀኔራል አብይ ሰናይ እባላለሁ::ምን አይነት አስጊ ሁኔታ ላይ እንዳለን ላስረዳሽ አልሞክርም፡፡ ምክንያቱም በሚገባ ትረጅዋለሽ፡፡ ስለሁኔታው ገለፃ እንደተደረገልሽ ተነግሮኛል፡፡ አልደግመውም፡፡ እንድትረጂኝ ነው የምጠይቅሽ…ቆይ ቆይ” አለ ሰውየው ርብቃ ልታቋርጠው ስትል ቀኝ እጁን ወደፊት ዘርግቶ፡፡ “አስጨርሽኝ፡፡ እንደተነገረሽ ናትናኤል የካልቨርትን ወዳጅ ገድሏታል፡፡
ስለካልቨርት ማንነት በቂ እውቀት እንዳለሽም ነግረውኛል፡፡ ስለዚህ ካልቨርት ስለወዳጁ መገደል ፍንጭ ከደረሰው እርሱ ራሱ እንደዛተው ምሥጢራችንን በቀጥታ በውጪ የስለላ ድርጅቶች አሰበለዚያም ለጋዜጠኞች ነው አሳልፎ የሚሰጠው:: ይህ ምን እንደሚያስከትል ከእኔ እኩል ትረጅዋለሽ፡፡ እርግጥ የሴትየዋን እሬሳ ለጊዜው ሰውረነዋል፡፡በቤቷም ውስጥ ያሉ ሴቶች
ስለሁኔታው እንዳይረዱና እንዳያወሩ የሚቻለው ሁሉ እየተደረገ ነው፡፡ ነገር
ግን አሁንም አንድ እጃችን ያልገባ ውል አለ፡፡ናትናኤል የሴትየዋ ግድያ
በእኛ እንደተፈጸመ አድርጎ ለካልቨርት ሊያስተላልፍ ከቻለ ወይንም የካልቨ
ርትን አድራሻ ደርሶበት ከተገናኘውና ምሥጢሩን ከተረዳ ውጤቱ ለሁላ
ችንም ጥፋት ነው:: እመኝኝ በአሁኗ ሰዓት ናትናኤል ከካልቨርት የበለጠ አደገኛ ነው፤ ሊያጠፋን ይችላል፡፡ እጅግ አደገኛ ሰው ነው፡፡”
“እኔኮ…” አለች ርብቃ እንባዋ በዓኗኗ ሲሞላ ልትውጠው እየታገለች።
“ይገባኛል... ይገባኛል ስሁኔታሽ ተነግሮኛል፡፡” አለ ሰውየው ለአንድ አፍታ ዓይኖቹን ወደ ሆዷ ዝቅ አድርጎ፡፡ «እርግጥ ስህተት ቢሆንም አንዴ ተፈጽሟል። ያረገዝሽው ልጅ የእርሱ ነው፡፡ ለዚህም ነው ሕይወቱን ለአደጋ አሳልፈሽ መስጠቱ የከቀደሽ፤ ይገባኛል፡፡ ወደእዚህ የመጣሁት መሃል ላይ የምንስማማበትን መስመር ለመፍጠር ነው፡፡ አንቺ የት እንዳለ ትነግሪኛለሽ፡፡ አለበለዚያም አጥምጄ እንድይዘው ትረጂኛለሽ፡፡ እኔ ደግሞ በሕይወቱም ላይ ሆነ በአካል ማንኛውም ዓይነት አደጋ እንደማይደርስበት ቃል እገባልሻሁ፡፡ እጃችን እንደገባ እዚህ እናመጣዋለን ወይም አንቺን እርሱን ወደምናቆይበት ስፍራ ፡ እንወስድሻለን፡፡ ለጊዜው ብቻ በቁጥጥር ስር እናቆየዋለን፡፡ ዕቅዳችንን ከውጤት ልናደርስ የቀረን አጭር ጊዜ ነው፡፡ከስድስት ቀን በኋላ አደገኛነቱ ያከትማል፡፡ ሁለታችሁም ነፃ ናችሁ፤ ቃል
እገባልሻለሁ:: ትስማሚያለሽ?” ጎንበስ ብሎ ጉልበቷን በወዳጅነት ስሜት ያዝ!
አደረገው፡፡
“የት እንደተደበቀ አላውቅም...
የት ብዬ ልናገር? "
“ግድ የለም ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ዘጠኝ ሰዓት ላይ መሥሪያ ቤትሽ ጓደኛሽጋ ደውሎ ነበር:: ስላንቺ ማሰቡንም ነግሯታል፡፡ ትንሽ መታመምሽንና ቤትሽ ስልክ ደውሎ ቢያነጋግርሽ እንደሚሻል እንድትነግረው አድርገናል፡፡ በማንኛውም ሰዓት እዚህ ሊደወል ይችላል፡፡ በሚደውልበት ሰዓት በጠና መታመምሽንና እንዲያይሽ መፈለግሽን እስተዛዝነሽ ትነግሪዋለሽ፡፡ በተቻለ መጠን ወጥመዳችን ውስጥ እንዲገባ ታባብያዋለሽ፡፡” ክንዷን ያዝ አድርጎ ተናገሪ- ::
ርብቃ በረጅሙ ተነፈሰች፡፡ ጭንቅላቷ እርስ በእርሱ ይጨቃጨቅ ይከራከር ጀመር... ይገድሉታል እውነት ከሆነ «ሰው ገደለ» ያሉት እውነት ከሆነ አይተውትም.. ሲያታልሏት ነው ሊያግባቧት ነው መስማማት የለባትም…እምቢ ብትል የሚከተላትን ስታስብ አይኖቿ በእንባ ተዘፈቁ፡፡ ያስቃይዋታል.ይደበድቧታል… ያንገላቷታል...
“ጊዜ የለንም... በማንኛውም ደቂቃ ሊደውል ይችላል፡፡ እመኚኝ እጄ እንዲገባ እርጅኝ፣ ቃሌን እጠብቃለሁ፡፡”
“አልችልም::” አለችው እንባዋ በጉንጮቿ እየወረደ፡፡
“ቃሌን ማንም ሊሽረው አይችልም! እመኚኝ፡፡ የምነግርሽ እውነት ነው፡፡ አንዲት ፀጉሩ ከላዩ እትወድቅም፡፡”
“አላምንም ሁላችሁንም ኣላምንም፡፡ ጓደኛውን ገድላችሁታል፡፡ አይደለም? እሱንም አትተውትም፡፡” ድምጿ በጭንቅ ቃተተ፡፡
ከቃሌ በላይ ልሰጥሽ የምችለው ማስተማመኛ የለኝም..ቃሌ ደግሞ
እውነት ነው::”
“አላምንም! ውሸት ነው! ውሽት ነው! ውሸት ነወ፡!…” እንዳትሸነፍ፡
የፈራች ይመስል አይኖቿን ጨፍና ጭንቅላቷን ቀኝና ግራ አላጋችው::
“ስለምንሽ ካልረዳሽኝ አስገድጄሽ የምፈልገውን : እንድትፈጽሚ
ማድረግ እችላለሁ።” ለመጀመሪያ ጊዜ ድምፁ ውስጥ የነበረ ልስላሴ
ሲቆረፍድ ተሰማት፡፡
“አልችልም! ልትገድሉኝ ትችላላችሁ፡፡አይኔ እያየ ለሞቱ አልጠራውም... ግደለኝ!” ሰውነቷን ነዘራት::
“አልገድልሽም፡፡ ያ ፍጹም ስህተት ነው አለ ሰውየው ከተቀመጠበት በእርጋታ እየተነሳ፡፡
ከጀርባው ለቆሙት ሰዎች ምልክት ከሰጣቸው በኋላ ሰእርጋታ ወደ
መስኮቱ ተጠግቶ ውጭ ወጪውን ይመለከት ጀመር፡፡ ከወንበሯ ላይ
ለሁለት ተሸክመው አንስተው ኣልጋዋ ላይ አጋደሟት፡፡ በፍጥነት አፏን ፈልቅቀው ቡትቶ ጨርቅ ጠቅጥቀው ለጎሟት፡፡ኣንዴ ብቻ “ማርቆስ!” አለች በጭንቀት…ያ የምታውቀው የሚያውቃት የህዋሷ መሪ ያግዝላት፣ ያድናት ይመስል፡፡ ከቆመበት አልተነቃነቃም::በጭንቅ የሚውጠው
ማንቁርቱን እላይ እታች ሲያመላልሰው የተጨነቀላት፣ ያዘነላት መሰላት፡፡
ተስፋ አደረገች፡፡ ትክ ብሎ ሲመለከታት ኣይኖቹ እንባ ያቆረዘዙ፡ መሰላት::
ተስፋ አደረገች፡፡ ማርቆስ ግን ከአልጋዋ በስተቀኝ ፈንጠር ብሎ እንደቆመ
ቀረ፡፡ አፏ ሲለጎም ልሳኗ ሲከዳት በአይኖችዋ ተማፀነች::: ዓይኖቹን
ከአይኖቿ ነቅሎ ትንፋሹን እላይ እታች እያመላለሰ ቆሞ ቀረ፡፡ ተስፋ ቆረጠች:: ለማይቀረው ዱላና ስቃይ ተዘጋጅታ ተጋደመች፡፡ ተጠባበቀች….
ኣልጋዎ ላይ ያጋደሟት ሰዎች እጆቿኝ ግራና ቀኝ ከአልጋው ጠርዝ ጋር
ጠፍረው ካሰሯት በኋላ የለበሰችውን ውሃ የበሰበሰ ስስ ቀሚስ ክላይዋ ላይ
እንደ ወረቀት እየቀዳደዱ ያነሱት ጀመር፡፡ ድንገት ሴትነቷ ገንፍሏት ወጣ፡፡
እግሮቿን እያፈራገጠች ወገቧን እየሰበቀች ቀሚሷን እላይዋ ላይ ለማስቀረት
ታገለች… ቀሚሷን ግን ኣላተረፈችውም፡፡ እግሮቿን ግራና ቀኝ በርግደው
ከአልጋው ጠርዞች ጋር ጠፈሯቸው...
የተሰማትን ህፍረት፣ የተሰማትን ውርደት ያጥብላት ይመስል እንባዋ ያለማቋረጥ በዓይኗ ጎንና ጎን ተዥጎደጎደ፡፡ ሃሞቷ ሆዷ ውስጥ የፈሰሰ ይመስል ሰውነቷ በመራራ ተሞላ፡፡ግራና ቀኝ ተበርግደው የታሰሩ
እግሮቿን ከታሰሩበት ገመድ ጋር እያፋተገች ሰውነቷን፣ ሴትነቷን፣
ለመሽፈን፣ ለመደበቅ፣
👍1👎1
ለመሽሽግ ታገለች፡፡ ገመዶቹ ግን አልተሸነፉላትም….
“ስልክ በማደወል ስዓት በጠና መታመምሽን አስተዛዝነሽ ትነግሪዋ
ለሽ…” ፊቱን ሳይመልስ በመስኮቱ ውጭ ውጭውን እየተመለከት በእርጋታ
ተናገራት:: መጥቶ እንዲያይሽም ትጎፋፊዋለሽ፡፡የመረጥሽውን መንገድ
ተጣቀሚ ተለማመጪው፤ለምኝው፤ አልቅሽ፡፡ መምጣት አለበት።ያንን ብቻ
አስታውሽ፡፡ ይህ ደግሞ የእኔ ብቻ ሳይሆን የአንቺም ፍላጎት ነው፡፡ ምክንያቱም ሳይመጣ ቢቀር ለሚቀጥሉት በርካታ ቀናት መጥፎ ነገር ታያለሽ፡፡እመኚኝ፡፡ ከዚያ በኋላ ቀሪ ሕይወት ቢኖርሽ እንኳን ልትኖሪው ፈቃደኛ አትሆኝም፡፡” ፊቱን መልሶ ቆመና ትክ ብሎ ተመለከታት፡፡ ወዲያው ከአልጋዋ በስተቀኝ ከቆሙት ሁለት ሰዎች ለኣንደኛው ምልክት ሰጠው፡፡
በስተቀኟ የቆመውን ሰው ከደረበው ጥቁር ቆዳ ጃኬት የውስጥ ኪስ
ውስጥ እስክሪብቶ የምትመስል ዕቃ አውጥቶ በአንደኛው ጫፉ በከል ክንድ
እስክታክል ድረስ መዘዛት፡፡ከቀኝ ኪሱ ውስጥ አነስተኛ የሲጋራ መለኮሻ
አውጥቶ ከለኮሰው ሰኋላ የመዘዛትን ቀጭን ሽቦ ጫፍ በእሳቱ ላይ
እሳረፋት፡፡ ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ውስጥ ቀጭኗ ሽቦ በቁመቷ: ሙሉ ከጫፍ
እስከጫፍ ግላ ፍም መሰለች፡፡ጠጣር ብረት መሆኗ ቀርቶ ፈሳሽ እሳት
እስክትመስል ድረስ ተንቀለቀለች፡፡ በዙሪያዋ ቀይ ብርሃን እስኪያንገርብብ
ጋመች፡፡
ሰውየው ቀጭኗ ሽቦ ፍም መምስሏን ሲመለከት የሲጋራ መለኮሻውን አጥፍቶ የጋለችውን ሽቦ ወደፊት ይዞ ወደ እግሮቿ መሃል ቀረበ፡፡ ጉልበቶቿ መሃል ገባ፡፡
ተወራጨች፡፡ ከቆመችው ሽቦ ለመሽሽ በተቻላት ሰውነቷን ከአልጋው ጋር አጣበቀችው:: ሽቦዋ ግን በቀስታ በጭንና ጭኖቿ መሃል ወደ
ሰውነቷ እየቀረበቻት መጣች… ጭንቅላቷን አርገፈገፈችው…ቃተተች…
“እመኚኝ የምናደርውን አትወጅውም ያህንንም ውሸት ነው ትያለሽ? ቃሌን እስካልፈጸምሽ ድረስ የሚከተለውን አትወጀውም፡፡” ጀርባውን ለመስኮቱ እንደሰጠ አሻግሮ ተመለከታት፡፡
በፍርሃት ተርበተበተች፡፡ በእርጋታ እየተራመደ : ወደ አልጋዋ ተጠጋ። ቀኝ እጁን እራቁት ትከሻዋ ላይ ጭኖ እንደ ህፃን ልጅ በሃዘኔታ ቁልቁል ተመለከታት፡፡
ባልኩሽ ሃሳብ ትስማሚያለሽ፣ ሲደውል ረጋ ብሰሽ ታነጋግሪዋለሽ፡፡መፍራት የለበትም፣ ቢሆንም በመጠኑ መደንገጥ አለበት:: መታመምሽንና ሊያይሽ እንደምትፈልጌ አስተዛዝነሽ ታስረጅዋለሽ፡ ታባብይዋለሽ፡፡”
ሰውነቷን ሳታነቃንቅ ዓይኖቿን ብቻ በፍርሃት እያቁለጨለጨች ሽቅብ ተመለከተችው፡፡
ወደፊት ጎንበስ ብሎ ከማጅራቷ የተቋጠረውን ጨርቅ ፈትቶ አፏ
ውስጥ የታጎስጎስውን ቡትቶ እወጣላት፡፡
“አይዞሽ ጥርጣሬ አይግባሽ፡፡ ልንጎዳሽ አንሻም:: ዛሬም ነገም ባልንጀሮችሽ ነን፡፡ ለአንድ ዓላማ የቆምን ነን፡፡ ያንን ሰይጣን ያንን ነፍስ ገዳይ ብቻ እጄ አግቢልኝ፡፡”
“ሠይጣን አንተ ነህ!” ድንገት ዛር ፈለቀባት፡፡ “ነፍሰ ገዳይ አንተ ነህ! እንኳን እጅህ ላገባልህ አጠገቡ አትደርስም ቱፍ! አፏ ውስጥ በተጠራቀመው መራራ ምራቅ ፊቱን ሸፈነችው:: በጥፊ ሲያግላት ያለችበት ተዘበራረቀባት፡፡ እግሮቿ መሃል ሲቡ ተሰማት:: ሽቦዋ.. ሽቦዋ፡፡.....
💫ይቀጥላል💫
“ስልክ በማደወል ስዓት በጠና መታመምሽን አስተዛዝነሽ ትነግሪዋ
ለሽ…” ፊቱን ሳይመልስ በመስኮቱ ውጭ ውጭውን እየተመለከት በእርጋታ
ተናገራት:: መጥቶ እንዲያይሽም ትጎፋፊዋለሽ፡፡የመረጥሽውን መንገድ
ተጣቀሚ ተለማመጪው፤ለምኝው፤ አልቅሽ፡፡ መምጣት አለበት።ያንን ብቻ
አስታውሽ፡፡ ይህ ደግሞ የእኔ ብቻ ሳይሆን የአንቺም ፍላጎት ነው፡፡ ምክንያቱም ሳይመጣ ቢቀር ለሚቀጥሉት በርካታ ቀናት መጥፎ ነገር ታያለሽ፡፡እመኚኝ፡፡ ከዚያ በኋላ ቀሪ ሕይወት ቢኖርሽ እንኳን ልትኖሪው ፈቃደኛ አትሆኝም፡፡” ፊቱን መልሶ ቆመና ትክ ብሎ ተመለከታት፡፡ ወዲያው ከአልጋዋ በስተቀኝ ከቆሙት ሁለት ሰዎች ለኣንደኛው ምልክት ሰጠው፡፡
በስተቀኟ የቆመውን ሰው ከደረበው ጥቁር ቆዳ ጃኬት የውስጥ ኪስ
ውስጥ እስክሪብቶ የምትመስል ዕቃ አውጥቶ በአንደኛው ጫፉ በከል ክንድ
እስክታክል ድረስ መዘዛት፡፡ከቀኝ ኪሱ ውስጥ አነስተኛ የሲጋራ መለኮሻ
አውጥቶ ከለኮሰው ሰኋላ የመዘዛትን ቀጭን ሽቦ ጫፍ በእሳቱ ላይ
እሳረፋት፡፡ ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ውስጥ ቀጭኗ ሽቦ በቁመቷ: ሙሉ ከጫፍ
እስከጫፍ ግላ ፍም መሰለች፡፡ጠጣር ብረት መሆኗ ቀርቶ ፈሳሽ እሳት
እስክትመስል ድረስ ተንቀለቀለች፡፡ በዙሪያዋ ቀይ ብርሃን እስኪያንገርብብ
ጋመች፡፡
ሰውየው ቀጭኗ ሽቦ ፍም መምስሏን ሲመለከት የሲጋራ መለኮሻውን አጥፍቶ የጋለችውን ሽቦ ወደፊት ይዞ ወደ እግሮቿ መሃል ቀረበ፡፡ ጉልበቶቿ መሃል ገባ፡፡
ተወራጨች፡፡ ከቆመችው ሽቦ ለመሽሽ በተቻላት ሰውነቷን ከአልጋው ጋር አጣበቀችው:: ሽቦዋ ግን በቀስታ በጭንና ጭኖቿ መሃል ወደ
ሰውነቷ እየቀረበቻት መጣች… ጭንቅላቷን አርገፈገፈችው…ቃተተች…
“እመኚኝ የምናደርውን አትወጅውም ያህንንም ውሸት ነው ትያለሽ? ቃሌን እስካልፈጸምሽ ድረስ የሚከተለውን አትወጀውም፡፡” ጀርባውን ለመስኮቱ እንደሰጠ አሻግሮ ተመለከታት፡፡
በፍርሃት ተርበተበተች፡፡ በእርጋታ እየተራመደ : ወደ አልጋዋ ተጠጋ። ቀኝ እጁን እራቁት ትከሻዋ ላይ ጭኖ እንደ ህፃን ልጅ በሃዘኔታ ቁልቁል ተመለከታት፡፡
ባልኩሽ ሃሳብ ትስማሚያለሽ፣ ሲደውል ረጋ ብሰሽ ታነጋግሪዋለሽ፡፡መፍራት የለበትም፣ ቢሆንም በመጠኑ መደንገጥ አለበት:: መታመምሽንና ሊያይሽ እንደምትፈልጌ አስተዛዝነሽ ታስረጅዋለሽ፡ ታባብይዋለሽ፡፡”
ሰውነቷን ሳታነቃንቅ ዓይኖቿን ብቻ በፍርሃት እያቁለጨለጨች ሽቅብ ተመለከተችው፡፡
ወደፊት ጎንበስ ብሎ ከማጅራቷ የተቋጠረውን ጨርቅ ፈትቶ አፏ
ውስጥ የታጎስጎስውን ቡትቶ እወጣላት፡፡
“አይዞሽ ጥርጣሬ አይግባሽ፡፡ ልንጎዳሽ አንሻም:: ዛሬም ነገም ባልንጀሮችሽ ነን፡፡ ለአንድ ዓላማ የቆምን ነን፡፡ ያንን ሰይጣን ያንን ነፍስ ገዳይ ብቻ እጄ አግቢልኝ፡፡”
“ሠይጣን አንተ ነህ!” ድንገት ዛር ፈለቀባት፡፡ “ነፍሰ ገዳይ አንተ ነህ! እንኳን እጅህ ላገባልህ አጠገቡ አትደርስም ቱፍ! አፏ ውስጥ በተጠራቀመው መራራ ምራቅ ፊቱን ሸፈነችው:: በጥፊ ሲያግላት ያለችበት ተዘበራረቀባት፡፡ እግሮቿ መሃል ሲቡ ተሰማት:: ሽቦዋ.. ሽቦዋ፡፡.....
💫ይቀጥላል💫
Forwarded from ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
#ሌሎች_እንዲያነቡትና_እንድማሩበት_አስተማሪ_ሆኖ_ካገኛችሁ_ሼር_ያድርጉ❗❗❗
#ስንት _ዓመት_ተማርን?
❖አሁን የምንሰራው ስራ ለሥጋዊ ኑሮ የሚሆን የሚጠቅም ነው በዚች ምድር ላይ ሳለን እንዳይርበን እንዳይጠማን እንዳይበርድን ኑሮአችን ለማመቻቸት እንወጣለን እንወርዳለለን🤔
✟👉✥ከሕፃንነታችን ጀምሮ እንማራለን
ሶስት ዓመት ጊዜ ወስደን መዋእለ ሕፃናት ተምረናል
👉 አስራ ሁለት ዓመት ጊዜ ሰጥተን 12 ክፍል ጨርሰናል(አቋርጠንም ያለን ልንኖር እንችላለን
👉 አምስት ዓመት በላይ ጊዜ ሰጥተን በድግሪ በማስተር ተመርቀናል
👉ባጠቃላይ የሥጋ ሥራ ለመያዝ ከሃያ ዓመት በላይ ተምረናል
🤔እንደዚህም ተምረን ስራ አጥተን በስራ ፍለጋ ደክመናል ወንድሜ(እህቴ) ሆይ አሁን ከ20 ዓመት በላይ የተማርነው ትምህርት ለስንት ዓመት ያሰራናል ?
🤔ጡረታ እስክንወጣ ነው ከዛ በሇላ የተማርነው ትምህርት አያገለግለንም
ከ20 ዓመት በላይ ስንማር የፈተፈተነው ጊዜ እናስብ ጭንቀቱን ድካሙን እንቅልፍ ማጣቱን
ከትምህርት ቤት ለመድረስ የእግር ጉዞውን ሁሉ አንርሳ ያ ሁሉ ደክመን የተማርከው ስንሞት አይጠቅመንም 🙊
🤔ሥጋችን መቃብር ሲገባ ምድራዊ እውቀታችን አብሮ ይቀበራል
👉በህይወት እያለን ጡረታ የምንወጣው መስራት አትችሉም ተብለን ነው
👉🤔ከ20 ዓመት በላይ በተማርነው ትምህርት ብንሰራበት 30 ዓመት ቢሆን ነው ያም እድሜ ከታደለህ ነው።
👉🤔ወንድሜ(እህቴ) ሆይ እስቲ ልጠይቃችሁ
ለሥጋችን ስራ ለመስራት ከ20 ዓመት በላይ ተምረናል
#ለነፍሳችን ስንት ዓመት ተማርን?
👉ለነፍሳችን የተማርነው ትምህርት ጡረታ የለውም
በሥጋ የተማርነው የመንግሥት ስራ ያስይዘናል
👉በነፍስ የተማርነው የእግዚአብሔር ስራ ያስይዘናል
የነፍስ ትምህርት ምን ይመስለናል ቃለ እግዚአብሔር ነው
✥#የእግዚአብሔርን ቃል በወር ስንት ሰዓት ተምረናል ?
👉✥በዓመት ስንት ቀን ይሆናል የተማርንበትም ጊዜ እስቲ እንደምረው?
✥ባጠቃላይ የተማርንበት ጊዜ እስክንሞትስ ስንት ዓመት ይሆናል?
👉✥ መቼም የሥጋውን የተምህርት ጊዜ አያክልም
✥በነፍስ የተማርነው ትምህርት ስንት ዓመት እንደሚያሰራልን እናውቃለን ?
✥ቁጥር የማይደርስበት ጊዜ ነው
ዘመናት አልፈነው እንሰራበታለን ለዘላለም ጡረታ አያወጣንም
👉✥እኛ ግን ይሄን ረስተናል ቀኑን ሙሉ ለሥጋችን እንሮጣለን ለነፍሳችን የምንማርበት ጌዜ አጥተናል በሚያልፈው ነገር እራሳችንን ቢዚ አድርገናል ::
👉✥ሁለት ሰኣት ቁጭ ብለን የተለያዩ ፊልም እናያለን 30 ደቂቃ ቁጭ ብለን ወንጌል መማር ይሰለቸናል::
👉✥ሁለት ሰአት ቆመን እያጨበጨብን ኳስ እንደግፋለን 2 ሰአት ቆመን ቅዳሴ ማስቀደስ አቅቶን በዕለተ ሰነበት ተኝተን እናረፍዳለህን
👉✥ልብ ወለድ ዝሙታዊ የሆኑ መጻፎችን በየቀኑ እናነባለን የእግዚአብሔር እስትንፋስ የሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍን ለማንበብ ይሰለቸናል
👉✥ለዘፈን የከፈትነውን አፋችንን ለምስጋና ይዘጋል
👉✥ለሀሜት የሚፈጥነው አፋችን ለጸሎት ይዘገያል
👉✥ለእስፓርት የጠነከረው ጉልበታችን ለስግደት ይዝላል
👉✥ለስርቆት የሚላከው እጃችን ለምጽዋት አይታዘዝም
👉✥ወደጭፈራ ቤት የሚገሰግሰው እግራችን ወደ ቤተክርስቲያን ለመሄድ ይተሰሰራል
👉✥ሀሜት የሚሰማው ጆሮአችን ወንጌል ለመስማት ይደነቁራል
👉✥የዝሙት ሸቶ የሚያሸተው አፍንጫችን የመቅደሱን እጣን ሽታ ይፀየፈዋል
👉✥ጫት የለመደው አፋችን ሥጋውን እና ደሙን ረስቶአል
👉✥አልኮል የለመደው አፋችን ፀበሉን ተፀይፎታል
👉✥ ቂም የሚቋጥረው ልባችን ፍቅርን ረስቷል
🤔✥ስናጣ እግዚአብሔርን እንቀርበዋለን ስናገኝ ግን እንርቀዋለን
🤔👉ስንጨነቅ አምላካችንን እንጠራዋለን ስንደሰት እንረሳዋለን
🤔✥ወንድሜ(እህቴ) ሆይ በህይወታችን አንቀልድባት
👉✥ከእኛ በፊት የነበሩት ተዋቂው አዋቂው ሁሉ የት አሉ? 👉✥መቃብር ውስጥ አይደሉምን ?
✟✥✟ይህንን አስበን ከፈጣሪያችን ጋር የሚያገናኝ ስራ እንስራ
✟✥✟ በአዲስ ዓመት አዲስ እቅድ ያስፈልገናል
✟✥✟ወደቤተ ክርስቲያን ሄደን ዘወትር ወንጌል እንማር
✟✥✟ ለማስቀደስ ለመፆም ለመስገድ እንትጋ
✟✥✟ ለንስሐ እንዘጋጅ ቅድሚያ ለነፍሳችን ሁሉን ነገር እናድርግ
❖አንደበታችን ለጸሎት ይትጋ
❖እጅአችን ለምጽዋት ይዘርጋ
❖ልባችን ለምህረት ይነሳሳ
❖ሥጋውን እና ደሙን ለመቀበል እንወስን
👉👉✥ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከአካፈልኩ በኁላ ቻነላችንን ይቀላቀሉ
@Z_TEWODROS
ሌሎችም እንድማሩበት #ሸር ያድርጉ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔም ጸልዩ!
✥"ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ይቆየን
#ሌሎች_እንዲያነቡትና_እንድማሩበት_አስተማሪ_ሆኖ_ካገኛችሁ_ሼር_ያድርጉ!
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
💚 •✥• @Z_TEWODROS •✥•💚
💛 •✥• @Z_TEWODROS •✥•💛
💖 •✥• @Z_TEWODROS •✥• 💖
#ስንት _ዓመት_ተማርን?
❖አሁን የምንሰራው ስራ ለሥጋዊ ኑሮ የሚሆን የሚጠቅም ነው በዚች ምድር ላይ ሳለን እንዳይርበን እንዳይጠማን እንዳይበርድን ኑሮአችን ለማመቻቸት እንወጣለን እንወርዳለለን🤔
✟👉✥ከሕፃንነታችን ጀምሮ እንማራለን
ሶስት ዓመት ጊዜ ወስደን መዋእለ ሕፃናት ተምረናል
👉 አስራ ሁለት ዓመት ጊዜ ሰጥተን 12 ክፍል ጨርሰናል(አቋርጠንም ያለን ልንኖር እንችላለን
👉 አምስት ዓመት በላይ ጊዜ ሰጥተን በድግሪ በማስተር ተመርቀናል
👉ባጠቃላይ የሥጋ ሥራ ለመያዝ ከሃያ ዓመት በላይ ተምረናል
🤔እንደዚህም ተምረን ስራ አጥተን በስራ ፍለጋ ደክመናል ወንድሜ(እህቴ) ሆይ አሁን ከ20 ዓመት በላይ የተማርነው ትምህርት ለስንት ዓመት ያሰራናል ?
🤔ጡረታ እስክንወጣ ነው ከዛ በሇላ የተማርነው ትምህርት አያገለግለንም
ከ20 ዓመት በላይ ስንማር የፈተፈተነው ጊዜ እናስብ ጭንቀቱን ድካሙን እንቅልፍ ማጣቱን
ከትምህርት ቤት ለመድረስ የእግር ጉዞውን ሁሉ አንርሳ ያ ሁሉ ደክመን የተማርከው ስንሞት አይጠቅመንም 🙊
🤔ሥጋችን መቃብር ሲገባ ምድራዊ እውቀታችን አብሮ ይቀበራል
👉በህይወት እያለን ጡረታ የምንወጣው መስራት አትችሉም ተብለን ነው
👉🤔ከ20 ዓመት በላይ በተማርነው ትምህርት ብንሰራበት 30 ዓመት ቢሆን ነው ያም እድሜ ከታደለህ ነው።
👉🤔ወንድሜ(እህቴ) ሆይ እስቲ ልጠይቃችሁ
ለሥጋችን ስራ ለመስራት ከ20 ዓመት በላይ ተምረናል
#ለነፍሳችን ስንት ዓመት ተማርን?
👉ለነፍሳችን የተማርነው ትምህርት ጡረታ የለውም
በሥጋ የተማርነው የመንግሥት ስራ ያስይዘናል
👉በነፍስ የተማርነው የእግዚአብሔር ስራ ያስይዘናል
የነፍስ ትምህርት ምን ይመስለናል ቃለ እግዚአብሔር ነው
✥#የእግዚአብሔርን ቃል በወር ስንት ሰዓት ተምረናል ?
👉✥በዓመት ስንት ቀን ይሆናል የተማርንበትም ጊዜ እስቲ እንደምረው?
✥ባጠቃላይ የተማርንበት ጊዜ እስክንሞትስ ስንት ዓመት ይሆናል?
👉✥ መቼም የሥጋውን የተምህርት ጊዜ አያክልም
✥በነፍስ የተማርነው ትምህርት ስንት ዓመት እንደሚያሰራልን እናውቃለን ?
✥ቁጥር የማይደርስበት ጊዜ ነው
ዘመናት አልፈነው እንሰራበታለን ለዘላለም ጡረታ አያወጣንም
👉✥እኛ ግን ይሄን ረስተናል ቀኑን ሙሉ ለሥጋችን እንሮጣለን ለነፍሳችን የምንማርበት ጌዜ አጥተናል በሚያልፈው ነገር እራሳችንን ቢዚ አድርገናል ::
👉✥ሁለት ሰኣት ቁጭ ብለን የተለያዩ ፊልም እናያለን 30 ደቂቃ ቁጭ ብለን ወንጌል መማር ይሰለቸናል::
👉✥ሁለት ሰአት ቆመን እያጨበጨብን ኳስ እንደግፋለን 2 ሰአት ቆመን ቅዳሴ ማስቀደስ አቅቶን በዕለተ ሰነበት ተኝተን እናረፍዳለህን
👉✥ልብ ወለድ ዝሙታዊ የሆኑ መጻፎችን በየቀኑ እናነባለን የእግዚአብሔር እስትንፋስ የሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍን ለማንበብ ይሰለቸናል
👉✥ለዘፈን የከፈትነውን አፋችንን ለምስጋና ይዘጋል
👉✥ለሀሜት የሚፈጥነው አፋችን ለጸሎት ይዘገያል
👉✥ለእስፓርት የጠነከረው ጉልበታችን ለስግደት ይዝላል
👉✥ለስርቆት የሚላከው እጃችን ለምጽዋት አይታዘዝም
👉✥ወደጭፈራ ቤት የሚገሰግሰው እግራችን ወደ ቤተክርስቲያን ለመሄድ ይተሰሰራል
👉✥ሀሜት የሚሰማው ጆሮአችን ወንጌል ለመስማት ይደነቁራል
👉✥የዝሙት ሸቶ የሚያሸተው አፍንጫችን የመቅደሱን እጣን ሽታ ይፀየፈዋል
👉✥ጫት የለመደው አፋችን ሥጋውን እና ደሙን ረስቶአል
👉✥አልኮል የለመደው አፋችን ፀበሉን ተፀይፎታል
👉✥ ቂም የሚቋጥረው ልባችን ፍቅርን ረስቷል
🤔✥ስናጣ እግዚአብሔርን እንቀርበዋለን ስናገኝ ግን እንርቀዋለን
🤔👉ስንጨነቅ አምላካችንን እንጠራዋለን ስንደሰት እንረሳዋለን
🤔✥ወንድሜ(እህቴ) ሆይ በህይወታችን አንቀልድባት
👉✥ከእኛ በፊት የነበሩት ተዋቂው አዋቂው ሁሉ የት አሉ? 👉✥መቃብር ውስጥ አይደሉምን ?
✟✥✟ይህንን አስበን ከፈጣሪያችን ጋር የሚያገናኝ ስራ እንስራ
✟✥✟ በአዲስ ዓመት አዲስ እቅድ ያስፈልገናል
✟✥✟ወደቤተ ክርስቲያን ሄደን ዘወትር ወንጌል እንማር
✟✥✟ ለማስቀደስ ለመፆም ለመስገድ እንትጋ
✟✥✟ ለንስሐ እንዘጋጅ ቅድሚያ ለነፍሳችን ሁሉን ነገር እናድርግ
❖አንደበታችን ለጸሎት ይትጋ
❖እጅአችን ለምጽዋት ይዘርጋ
❖ልባችን ለምህረት ይነሳሳ
❖ሥጋውን እና ደሙን ለመቀበል እንወስን
👉👉✥ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከአካፈልኩ በኁላ ቻነላችንን ይቀላቀሉ
@Z_TEWODROS
ሌሎችም እንድማሩበት #ሸር ያድርጉ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔም ጸልዩ!
✥"ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ይቆየን
#ሌሎች_እንዲያነቡትና_እንድማሩበት_አስተማሪ_ሆኖ_ካገኛችሁ_ሼር_ያድርጉ!
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
💚 •✥• @Z_TEWODROS •✥•💚
💛 •✥• @Z_TEWODROS •✥•💛
💖 •✥• @Z_TEWODROS •✥• 💖
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
.... የቢሊየነሩ ዊሊ ባደን ውሽማ የነበረችው ሊዛ ፍላንግ ከዚህች ከዶክተር ሮበርትስ ጋ ህክምና ትወስድ እንደነበረ
ለማወቅ ያገዙት እነዚያ የግድያ ዜናውን የሚያራግቡት ሚዲያዎች ነበሩ።
ለሃያ ደቂቃ ያህል ጎግል ላይ ስለ ዶክተር ኤኮላስ ሮበርትስ የሰበሰበው መረጃ
ዶክተሯ በምዕራብ ሎስ አንጀለስ ውስጥ የምትኖር፣ በሙያዋ የምትከበር እና
ባለፈው ዓመትም ባሏ ዶክተር ዶውግላስን በሞት ያጣች ሴት እንደሆነች
ለማወቅ ችሏል፡፡ ይሄ ደግሞ እሷን የተጠየቀችውን መክፈል የምትችል ሰው
ያደርጋታል። በዚያ ላይ ደግሞ እስር ቤት እንዳይገባም ያቺ የተረገመች ዳኛ
የወሰነችለትን የልጁን ተቆራጭ ገንዘብ ማቋረጥ የለበትም፡፡ እናም ጥሩ
ገንዘብ ያስፈልገዋል። እንግዲህ ዕድሉን ቡናውን ሽሚዙ ላይ በመድፋቱ የተነሳ ያበላሸ አይመስለውም፡፡ ኒኪ እሱን ደንጋጣ ነው ብላ ካሰበችው ችግር
ሊፈጠርበት ይችላል፡፡
ለማንኛውም ኒኪ ሮበርትስ በራሷ ሀሳብ ውስጥ ስለነበረች ሊሆን ይችላል
እሱ እንደፈራው ቡና የደፋበትን ሁኔታ አላስተዋለችም፡፡ አጠገቡ ከሚገኝ
አንድ ወንበር ላይ ቁጭ አለች እና ከቦርሳዋ ውስጥ አንድ ኤንቨሎፕ
አውጥታ ሰጠችው።
“ከየት መጀመር እንዳለብኝ እርግጠኛ አይደለሁም። ስለዚህም ኢንቨሎፕ
ውስጥ ትናንሽ ማስታወሻዎችን ትቼልሀለሁ።” ብላ በመቀጠልም “ሚስተር ዊሊያምስ ያንተን እርዳታ እፈልጋለሁ። ያው ትላንትና ማታ እንደነገርኩህ ፖሊሶች ነፍሰ ገዳዩን ለመያዝ ምንም አይነት የተሻለ ነገር ሲያደርጉ አልታየኝም::” አለችው፡፡
“ዶክተር ሮበርትስ ኒኪ ይህንን የፖሊሶቹን የማይረባ ሥራ ለብዙ ጊዜ ሰምቼያለሁ” አላት እና ወደ እሷ አንገቱን አስግጎ በመጠጋትም “ኢንቨሎፕ ውስጥ ያለውን ነገር በኋላ ላየው እችላለሁ፡፡ ለአሁኑ ግን አንቺ ራስሽ ለምን ያለውን ነገር አትነግሪኝም?” አላት እና ዝም ብሎ ይመለከታት ጀመር።
ኒኪ ሁለመናውን መገምገም ጀመረች፡፡ ወፍራም፣ ፈዛዛ ቢጫ ቀለም ያለው ፊት፡፡ ዘገም ያለ የአካላዊ እንቅስቃሴን የሚያደርግ ሰው ነው።በውስጧም ምናልባት እሱ ሰካራም ምናልባትም ፈት እና ገንዘብ የሚያጥረው ሰው ነው ብላ ደመደመች። በእርግጥ ይህንን ግምቷን
ለማስቀመጥ የግድ አልበርት አንስታይንን መሆን አይጠበቅባትም።ምክንያቱም ማንም በከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ፕሮፌሽናል ሰው የቁርስ ላይ ቀጠሮውን እዚህ ርካሽ ከሆነው አይ ሆፕ ውስጥ እንደማይዝ መቼስ ይታወቃል አይደል?
ማታ ላይ ስለ ዴሪክ ዊሊያምስ የቀድሞ ደምበኞቹ ስለ እሱ ለማግኘት የማይፈነቅለው ነገር የለም። በዚህም የተነሳ ከአንድም ሁለት ጊዜ ከነገሮች በላይ (ከህግ በላይ) በጣም ገፍቶ በመሄድ የሚፈልገውን መረጃ
ፍርድ ቤት ቀርቧል። ይህንን አደጋን የመጋፈጥ እና ነገሮችን በጣም ገፍቶ
በመሄድ የሚሰራ ሰው እንደሆነ ስለምታውቅ ነበር ኒኪ እሱን የፈለገችው።
ወደ እሱ ደውላ ቀጠሮ የያዘችበት ዋነኛ ምክንያቷም የግል መርማሪውን ደፋርነት በማንበቧ ነው።
“እንደ ነገርኩህ እኔ ከየት መጀመር እንዳለብኝ አላውቅም” አለችው፡፡
“መጀመሪያ ነው ብለሽ ካሰብሽው ነገር ለምን አትጀምሪም?” አላት እና ዊሊያምስ ባልኮኒው ጋር ወደምትገኘው አስተናጋጅ አንድሪያን ዞሮ “የኔ ቆንጆ ቁርሴን የተጠበሰ እንቁላል ከጎኑ ደግሞ ፓንኬክ አድርጊልኝ፡፡ ለጓደኛዬ ደግሞ?” ብሎ ኒኪን ተመለከታት፡፡
“እኔ ቡና ብቻ ነው የምወስደው”
“ለእሷም እንቁላል ጥብስ ይሁንላት” አላት እና ዊሊያምስ በግርምት ወደምታየው ኒኪ ፊቱን መልሶ “የእኔ እመቤት መብላት ይኖርብሻል። ሰዎች
በኑሯቸው ዙሪያ ምን እየተካሄደ እንደሆነ ደውለው እኔን ካገኙ እና ጭንቀታቸውን ካረገፉ ምን ይቀራቸዋል? ስለዚህ አንቺ ምን ማድረግ አለብሽ መሰለሽ? በቃ በደንብ መብላት እና ሀሳብሽን ለእኔ ጥለሽ መተኛት ነው የሚኖርብሽ” አላት፡፡
ዴሪክ ዊሊያምስ በቅንነት ሀሳቡን ስለነገራትም ነው መሰል ኒኪ ተበረታታች እና ማውራት ጀመረች፡፡ “መልካም እንግዲህ... ከመጀመሪያው ጀምረሽ ንገሪኝ ብለኸኛል አይደል? ለእኔ እውነተኛው የመጀመሪያው ነገር
ምን መሰለህ? ሟቹ ባለቤቴ ከትዳሩ ውጪ የፍቅር ግንኙነት ነበረው” ብላ
ነገሯን ጀመረች፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ቫላንቲና ባደን የጂ 6 አውሮፕላኗ ጎማዎች ሜክሲኮ ካቦ ውስጥ
ከሚገኘው የሳን ሉካን አየር ማረፊያ ወለል ሲነኩ አምላኳ በሰላም ስላስገባት
የምስጋና ፀሎትን በውስጧ አደረገች፡፡
ቫለንቲና ብዙ ነገሮችን የምትፈራ ሴት አይደለችም። እህቷ ከ 50 ዓመት
በፊት ከጠፋችበት ጊዜ ጀምሮ በደንብ እስካሰበችባቸው ጊዜ ድረስ ያለፈቃዷ
ተፅዕኖ የሚያሳድሩ ነገሮች በጣም ጥቂት እንደሆኑ ለማወቅ ችላለች።
ወዳጆቿ በአውሮፕላን የመጓዝ ፍርሃቷ የመነጨው ነገሩን መቆጣጠር
እንደማትችል ከማመኗ የተነሳ እንደሆነ ግምታቸውን ያስቀምጣሉ።ምናልባት ትክክል ሊሆኑ ይችላሉ። ምክንያቱም ከበፊት ጀምሮ ቫለንቲና በትዳሯ፣ በቤተሰቧ፣ በምትሰራቸው ቢዝነሶቿ እና ከሰዎች ጋር ያሏትን ግንኙነቶች በሙሉ እሷ ሙሉ በሙሉ ስትቆጣጠራቸው ነው የኖረችው።
የሎስ አንጀለስ ቆይታዋ ስኬታማ ነበር። ሳይጠብቋት በድንገት ወደ በጎ
አድራጎት ድርጅቶቿ ቢሮዎች ጎራ ብላ ነበር። ቢሮዎቹ ውስጥ ገብታም
የድርጅቱን የተሳኩ የፍለጋ ሥራዎችን እንዲሁም ደግሞ የስድስት ወሩን
የተዘበራረቀ የባንክ ሂሳብ ሪፓርትን እንዲያሳዩአት ጠይቃ ለማየት ችላለች።
የአሜሪካ ውስጥ የገቢዎች ቢሮ የድርጅቱን ከውጪ የሚገቡለትን ገቢዎች
ምንጭ ማነፍነፍ ከጀመረ ወዲህ ቫለንቲና ራሷ ናት እነዚህ አይነት ነገሮችን
የምትቆጣጠረው። በድርጅቱ ውስጥ የሚሰሩ ጥቂት ሰዎች ብቻ ናቸው
እውነተኛው የሥራ አካሄዳቸውን ጠንቅቀው የሚያውቁት እና ሥራቸው
ሚስጥሩ ተጠብቆ መስራት እንዳለበት የሚገነዘቡት። ዊሊ ባሏ ደግሞ ሰነፍ
ስለሆነ እሷ የምትሰራቸው ሥራዎች ላይ አትኩሮት ሰጥቶ አያውቅም።ባለፈው ጊዜ ዊሊ ለኤል.ኤ ፖሊስ ክፍያ በመፈፀም ይደረግባቸው የነበረው
ምርመራ እንዲቋረጥ አድርጓል። የአሁኑ የአሜሪካ የውስጥ ገቢዎች አካሄድ
ግን ይለያል እና ቫለንቲና መጠንቀቅ እንደሚኖርባት ታውቃለች።
በዚያ ላይ ደግሞ እሷ በድንገት ቢሯቸው ውስጥ ገብታ እሷን ንግስታቸውን ለማስደስት የሚራኮቱትን ሰራተኞችን መመልከት ደስ ይላታል፡፡ የበጎ አድራጎት ሥራዎችም ልክ እንደ ሌሎች ለትርፍ የሚሠሩ ድርጅቶች ሁሉ የራሳቸው የሆነ መለኪያ እንዳላቸው፣ መለኪያዎቹም
ድርጅቱ የሚያስመዘግባቸው በጎ ውጤቶች መሆኑን ለሰራተኞቿ በየጊዜው
ነው የምትነግራቸው።
ለባለፉት አሥራ አምስት ዓመታትም በጣም በጣት ከሚቆጠሩት የፍለጋ
ሥራዎቻቸው በስተቀር ሁሉም በጥሩ ሁኔታ እንደተጠናቀቁ ስታስረዳቸው
በኩራት ነበር። ሬቼ ላምብ የተባለ ድክ ድክ የሚል ህፃን ቱርክ ውስጥ
ቤተሰቦቹ ለመዝናናት በሄዱበት ጊዜ ላይ ጠፍቶ አልተገኘም። የቻርሎቴ
ክላንሲ መጥፋት፣ የዚህች ወጣት ያለመገኘት ደግሞ ራሷን ቫለንቲናን
ጭምር ያሳዝናታል፡፡ ምክንያቱም ልጅቷ የጠፋችው ልክ እንደ ቫለንቲና መንታ እህት ሜክሲኮ ውስጥ ስለነበረ ቫለንቲና ልቧ ተነክቶ ነበር። ምንም እንኳን ውጤታቸው ፍሬ አልባ ቢሆንባቸውም፤ ከሌሎች የማፈላለግ ሂደቶች
በተለየ መልኩ በየሚድያዎቹ ላይ ስለ ክላንሲ እንዲነገር አድርጋ ነበር
ድርጅቷ በሁሉም የፍለጋ ሥራዎቻቸው ላይ መቋጫን ሳያበጁ ፍለጋውን
አያቋርጡም። ለምሳሌ ያህል የብራንዶን ግሮልሽን ፍለጋ የሚመስሉ አይነት
ሥራዎቻቸው ላይ የፈላጊ ቤተሰብን ልብ የሚሰብር አሳዛኝ ነገርንም መናገር
(ማሳወቅ)
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
.... የቢሊየነሩ ዊሊ ባደን ውሽማ የነበረችው ሊዛ ፍላንግ ከዚህች ከዶክተር ሮበርትስ ጋ ህክምና ትወስድ እንደነበረ
ለማወቅ ያገዙት እነዚያ የግድያ ዜናውን የሚያራግቡት ሚዲያዎች ነበሩ።
ለሃያ ደቂቃ ያህል ጎግል ላይ ስለ ዶክተር ኤኮላስ ሮበርትስ የሰበሰበው መረጃ
ዶክተሯ በምዕራብ ሎስ አንጀለስ ውስጥ የምትኖር፣ በሙያዋ የምትከበር እና
ባለፈው ዓመትም ባሏ ዶክተር ዶውግላስን በሞት ያጣች ሴት እንደሆነች
ለማወቅ ችሏል፡፡ ይሄ ደግሞ እሷን የተጠየቀችውን መክፈል የምትችል ሰው
ያደርጋታል። በዚያ ላይ ደግሞ እስር ቤት እንዳይገባም ያቺ የተረገመች ዳኛ
የወሰነችለትን የልጁን ተቆራጭ ገንዘብ ማቋረጥ የለበትም፡፡ እናም ጥሩ
ገንዘብ ያስፈልገዋል። እንግዲህ ዕድሉን ቡናውን ሽሚዙ ላይ በመድፋቱ የተነሳ ያበላሸ አይመስለውም፡፡ ኒኪ እሱን ደንጋጣ ነው ብላ ካሰበችው ችግር
ሊፈጠርበት ይችላል፡፡
ለማንኛውም ኒኪ ሮበርትስ በራሷ ሀሳብ ውስጥ ስለነበረች ሊሆን ይችላል
እሱ እንደፈራው ቡና የደፋበትን ሁኔታ አላስተዋለችም፡፡ አጠገቡ ከሚገኝ
አንድ ወንበር ላይ ቁጭ አለች እና ከቦርሳዋ ውስጥ አንድ ኤንቨሎፕ
አውጥታ ሰጠችው።
“ከየት መጀመር እንዳለብኝ እርግጠኛ አይደለሁም። ስለዚህም ኢንቨሎፕ
ውስጥ ትናንሽ ማስታወሻዎችን ትቼልሀለሁ።” ብላ በመቀጠልም “ሚስተር ዊሊያምስ ያንተን እርዳታ እፈልጋለሁ። ያው ትላንትና ማታ እንደነገርኩህ ፖሊሶች ነፍሰ ገዳዩን ለመያዝ ምንም አይነት የተሻለ ነገር ሲያደርጉ አልታየኝም::” አለችው፡፡
“ዶክተር ሮበርትስ ኒኪ ይህንን የፖሊሶቹን የማይረባ ሥራ ለብዙ ጊዜ ሰምቼያለሁ” አላት እና ወደ እሷ አንገቱን አስግጎ በመጠጋትም “ኢንቨሎፕ ውስጥ ያለውን ነገር በኋላ ላየው እችላለሁ፡፡ ለአሁኑ ግን አንቺ ራስሽ ለምን ያለውን ነገር አትነግሪኝም?” አላት እና ዝም ብሎ ይመለከታት ጀመር።
ኒኪ ሁለመናውን መገምገም ጀመረች፡፡ ወፍራም፣ ፈዛዛ ቢጫ ቀለም ያለው ፊት፡፡ ዘገም ያለ የአካላዊ እንቅስቃሴን የሚያደርግ ሰው ነው።በውስጧም ምናልባት እሱ ሰካራም ምናልባትም ፈት እና ገንዘብ የሚያጥረው ሰው ነው ብላ ደመደመች። በእርግጥ ይህንን ግምቷን
ለማስቀመጥ የግድ አልበርት አንስታይንን መሆን አይጠበቅባትም።ምክንያቱም ማንም በከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ ፕሮፌሽናል ሰው የቁርስ ላይ ቀጠሮውን እዚህ ርካሽ ከሆነው አይ ሆፕ ውስጥ እንደማይዝ መቼስ ይታወቃል አይደል?
ማታ ላይ ስለ ዴሪክ ዊሊያምስ የቀድሞ ደምበኞቹ ስለ እሱ ለማግኘት የማይፈነቅለው ነገር የለም። በዚህም የተነሳ ከአንድም ሁለት ጊዜ ከነገሮች በላይ (ከህግ በላይ) በጣም ገፍቶ በመሄድ የሚፈልገውን መረጃ
ፍርድ ቤት ቀርቧል። ይህንን አደጋን የመጋፈጥ እና ነገሮችን በጣም ገፍቶ
በመሄድ የሚሰራ ሰው እንደሆነ ስለምታውቅ ነበር ኒኪ እሱን የፈለገችው።
ወደ እሱ ደውላ ቀጠሮ የያዘችበት ዋነኛ ምክንያቷም የግል መርማሪውን ደፋርነት በማንበቧ ነው።
“እንደ ነገርኩህ እኔ ከየት መጀመር እንዳለብኝ አላውቅም” አለችው፡፡
“መጀመሪያ ነው ብለሽ ካሰብሽው ነገር ለምን አትጀምሪም?” አላት እና ዊሊያምስ ባልኮኒው ጋር ወደምትገኘው አስተናጋጅ አንድሪያን ዞሮ “የኔ ቆንጆ ቁርሴን የተጠበሰ እንቁላል ከጎኑ ደግሞ ፓንኬክ አድርጊልኝ፡፡ ለጓደኛዬ ደግሞ?” ብሎ ኒኪን ተመለከታት፡፡
“እኔ ቡና ብቻ ነው የምወስደው”
“ለእሷም እንቁላል ጥብስ ይሁንላት” አላት እና ዊሊያምስ በግርምት ወደምታየው ኒኪ ፊቱን መልሶ “የእኔ እመቤት መብላት ይኖርብሻል። ሰዎች
በኑሯቸው ዙሪያ ምን እየተካሄደ እንደሆነ ደውለው እኔን ካገኙ እና ጭንቀታቸውን ካረገፉ ምን ይቀራቸዋል? ስለዚህ አንቺ ምን ማድረግ አለብሽ መሰለሽ? በቃ በደንብ መብላት እና ሀሳብሽን ለእኔ ጥለሽ መተኛት ነው የሚኖርብሽ” አላት፡፡
ዴሪክ ዊሊያምስ በቅንነት ሀሳቡን ስለነገራትም ነው መሰል ኒኪ ተበረታታች እና ማውራት ጀመረች፡፡ “መልካም እንግዲህ... ከመጀመሪያው ጀምረሽ ንገሪኝ ብለኸኛል አይደል? ለእኔ እውነተኛው የመጀመሪያው ነገር
ምን መሰለህ? ሟቹ ባለቤቴ ከትዳሩ ውጪ የፍቅር ግንኙነት ነበረው” ብላ
ነገሯን ጀመረች፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ቫላንቲና ባደን የጂ 6 አውሮፕላኗ ጎማዎች ሜክሲኮ ካቦ ውስጥ
ከሚገኘው የሳን ሉካን አየር ማረፊያ ወለል ሲነኩ አምላኳ በሰላም ስላስገባት
የምስጋና ፀሎትን በውስጧ አደረገች፡፡
ቫለንቲና ብዙ ነገሮችን የምትፈራ ሴት አይደለችም። እህቷ ከ 50 ዓመት
በፊት ከጠፋችበት ጊዜ ጀምሮ በደንብ እስካሰበችባቸው ጊዜ ድረስ ያለፈቃዷ
ተፅዕኖ የሚያሳድሩ ነገሮች በጣም ጥቂት እንደሆኑ ለማወቅ ችላለች።
ወዳጆቿ በአውሮፕላን የመጓዝ ፍርሃቷ የመነጨው ነገሩን መቆጣጠር
እንደማትችል ከማመኗ የተነሳ እንደሆነ ግምታቸውን ያስቀምጣሉ።ምናልባት ትክክል ሊሆኑ ይችላሉ። ምክንያቱም ከበፊት ጀምሮ ቫለንቲና በትዳሯ፣ በቤተሰቧ፣ በምትሰራቸው ቢዝነሶቿ እና ከሰዎች ጋር ያሏትን ግንኙነቶች በሙሉ እሷ ሙሉ በሙሉ ስትቆጣጠራቸው ነው የኖረችው።
የሎስ አንጀለስ ቆይታዋ ስኬታማ ነበር። ሳይጠብቋት በድንገት ወደ በጎ
አድራጎት ድርጅቶቿ ቢሮዎች ጎራ ብላ ነበር። ቢሮዎቹ ውስጥ ገብታም
የድርጅቱን የተሳኩ የፍለጋ ሥራዎችን እንዲሁም ደግሞ የስድስት ወሩን
የተዘበራረቀ የባንክ ሂሳብ ሪፓርትን እንዲያሳዩአት ጠይቃ ለማየት ችላለች።
የአሜሪካ ውስጥ የገቢዎች ቢሮ የድርጅቱን ከውጪ የሚገቡለትን ገቢዎች
ምንጭ ማነፍነፍ ከጀመረ ወዲህ ቫለንቲና ራሷ ናት እነዚህ አይነት ነገሮችን
የምትቆጣጠረው። በድርጅቱ ውስጥ የሚሰሩ ጥቂት ሰዎች ብቻ ናቸው
እውነተኛው የሥራ አካሄዳቸውን ጠንቅቀው የሚያውቁት እና ሥራቸው
ሚስጥሩ ተጠብቆ መስራት እንዳለበት የሚገነዘቡት። ዊሊ ባሏ ደግሞ ሰነፍ
ስለሆነ እሷ የምትሰራቸው ሥራዎች ላይ አትኩሮት ሰጥቶ አያውቅም።ባለፈው ጊዜ ዊሊ ለኤል.ኤ ፖሊስ ክፍያ በመፈፀም ይደረግባቸው የነበረው
ምርመራ እንዲቋረጥ አድርጓል። የአሁኑ የአሜሪካ የውስጥ ገቢዎች አካሄድ
ግን ይለያል እና ቫለንቲና መጠንቀቅ እንደሚኖርባት ታውቃለች።
በዚያ ላይ ደግሞ እሷ በድንገት ቢሯቸው ውስጥ ገብታ እሷን ንግስታቸውን ለማስደስት የሚራኮቱትን ሰራተኞችን መመልከት ደስ ይላታል፡፡ የበጎ አድራጎት ሥራዎችም ልክ እንደ ሌሎች ለትርፍ የሚሠሩ ድርጅቶች ሁሉ የራሳቸው የሆነ መለኪያ እንዳላቸው፣ መለኪያዎቹም
ድርጅቱ የሚያስመዘግባቸው በጎ ውጤቶች መሆኑን ለሰራተኞቿ በየጊዜው
ነው የምትነግራቸው።
ለባለፉት አሥራ አምስት ዓመታትም በጣም በጣት ከሚቆጠሩት የፍለጋ
ሥራዎቻቸው በስተቀር ሁሉም በጥሩ ሁኔታ እንደተጠናቀቁ ስታስረዳቸው
በኩራት ነበር። ሬቼ ላምብ የተባለ ድክ ድክ የሚል ህፃን ቱርክ ውስጥ
ቤተሰቦቹ ለመዝናናት በሄዱበት ጊዜ ላይ ጠፍቶ አልተገኘም። የቻርሎቴ
ክላንሲ መጥፋት፣ የዚህች ወጣት ያለመገኘት ደግሞ ራሷን ቫለንቲናን
ጭምር ያሳዝናታል፡፡ ምክንያቱም ልጅቷ የጠፋችው ልክ እንደ ቫለንቲና መንታ እህት ሜክሲኮ ውስጥ ስለነበረ ቫለንቲና ልቧ ተነክቶ ነበር። ምንም እንኳን ውጤታቸው ፍሬ አልባ ቢሆንባቸውም፤ ከሌሎች የማፈላለግ ሂደቶች
በተለየ መልኩ በየሚድያዎቹ ላይ ስለ ክላንሲ እንዲነገር አድርጋ ነበር
ድርጅቷ በሁሉም የፍለጋ ሥራዎቻቸው ላይ መቋጫን ሳያበጁ ፍለጋውን
አያቋርጡም። ለምሳሌ ያህል የብራንዶን ግሮልሽን ፍለጋ የሚመስሉ አይነት
ሥራዎቻቸው ላይ የፈላጊ ቤተሰብን ልብ የሚሰብር አሳዛኝ ነገርንም መናገር
(ማሳወቅ)
👍2🔥1🥰1
) ይችላሉ። ለማንኛውም ድርጅቱ እንደዚህ አይነት ስኬቶችን
የመጎናፀፍ ምክንያቶች ቫለንቲና ሳታቋርጥ ስራተኞቿን በመሸለሟ እና
በመቅጣቷ የመጡ ስኬቶች ነበሩ።
የዚህ ሳምንት አሰራር ግን ቅጣትን መሰረት ያደረገ ነበር። ቢሮ ውስጥ
በቆየችባቸው የአንድ ሰአት ጊዜዋ ውስጥ አካውንታንቱ እና ረዳቶቹን ስታሸብር ነበር።
“ሥራዎች በአግባቡ እንዲከናወኑ ከፈለግክ ሥራውን አንተ ራስህ ስራው ብላ ቴሪ ኤንጀልስ የተባለውን የኤል.ኤ ኦፊስ ማናጀርን ወረፈችው።
“የባለፉት ስድስት ወራት ፋይሎች በሙሉ የማይረቡ እና ያልተደራጁ ናቸው። እዚህ በምቆይበት ጊዜ ላይም እኔው ራሴ አደራጃቸዋለሁ።በሚቀጥለው ጊዜ ግን እንደዚህ አይነት ጉዳይ ቢገጥመኝ ቦታህን ትለቃለህ”
የገንዘብ ነክ ጉዳዮች ላይ ያሏትን ሥራዎች ከጨረሰች በኋላ ቢሮው
ውስጥ ያልተገኙ ሠራተኞች ላይ ቅጣቶችን ወስና ከቢሮዋ ወጣች። ሌሎች ልትሠራቸው ያሰበቻቸውን ሥራዎችንም ሎስ አንጀለስ ውስጥ በቆየችባቸው ጊዜያት ላይ በደንብ አጠናቅቃ ወደ ሜክሲኮ ካቦ ተመለሰች። ሎስ አንጀለስ በቆየችባቸው ጊዜያት ላይ እሷን ቫለንቲና ባደንን ማንም ሰው ሊያሞኛት እንደማይችል ተገቢውን ትምህርት ለሁሉም ሰዎች ሰጥታ ወደ ካቦ ስለተመለሰች፤ ቆይታዋ ስኬታማ እንደሆነ ገምታ ጥሩ ስሜት ተሰማት።
ዊሊ ባደን በየጊዜው ወደ እሷ እየደወለ አሁን ላይ አብሮት እየሰራው በሚገኘው ሰው ላይ ያለውን ፍራቻ በመንገር ሲነዘንዛት ብቻ ትንሽ ምቾት አጥታ ነበር፡፡ አሁን ላይ የሚያስፈልጋቸው ነገር ቢኖር ሚድያዎች ስለ ሊዛ ፍላንገን እና ስለ ዊሊ የፍቅር ግንኙነት እንዲሁም ደግሞ ስለዚያች የተረገመች ሳይኮሎጂስት
ዶክተር ሮበርትስ የሚያወሩትን ነገሮች
እንዲያቆሙ ማድረግ ብቻ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ ግን ነገሮች ወደ ቀድሞ ሰላማዊ ሁኔታቸው ይመለሳሉ። .
“እግዚአብሔር ይመስገን እንኳን መጣሽልኝ” አላት ዊሊ ባደን ለቫለንቲና፡፡ ዊሊ ባደን ራሱ አውሮፕላን ማረፊያ ድረስ ሊቀበላት በመምጣቱ ትንሽ ገርሟታል። የታርማክ መኪናቸው ሹፌር የቫለንቲናን ቦርሳዎች ተቀብሏት መኪናው ውስጥ ካስገባ በኋላ መኪናውን መሾፈር ጀመረ።
ይሄኔም ዊሊ ባደን “ሁለት ቀን ሙሉ ስደውልለት እኮ ስልኩን አያነሳም!”
ብሎ ፍርሃት በወረረው ድምፅም “
ሰማሺኝ? ሁለት ቀን ሙሉ ስልክ
አያነሳም፡፡ በጣም ሳይናደድብኝ አልቀረም!” አላት፡፡
“ማን ነው የተናደደው?” ብላ ቫለንቲና ጠየቀችው፡፡
“ስለማን ነው እያወራሁኝ ያለሁት?” ብሎ በንዴት ጠየቃት፡፡
“ሮዲሪጉዜን ነው?” ብላ ቫለንቲና በረዥሙ ተነፈሰች።
“አዎ ሮዲሪጉዜ ነዋ!” ብሎ በፍርሃት ድምፀት ውስጥ ሆኖ “እሱ ጋር
ሥራ መሥራት አልነበረብንም፡፡ ይሄ የማይረባ ድርድር...” ብሎ
“ብዙ የሥራ ዕድልን እና ሀብትን ይዞልን ይመጣል።” ብላ ቫለንቲና እሱ ሊናገር ባላሰበው መልኩ መለሰችለት እና ክንዱን ጭምቅ አድርጋ በመያዝ “ዊሊ መረጋጋት ይኖርብሃል። በዚህ ጊዜ ላይ ፍራቻን ማሳየት የለብህም። እንደ ሮዲሪጉዜ ያሉ ሰዎች የሌሎች ሰዎችን ድክመት ልክ ሻርክ ደምን በሚያሸትበት ሁኔታ ነው የሚያሽቱት። ከእንደ እሱ አይነት ሰዎች ጋር እንዳደግኩኝ ነግሬሀለሁ አይደል? እዚህ ነገሮች በተለየ መልኩ ነው
የሚከወኑት።” አለችው፡፡
“እሱንማ አውቃለው” በማለት ዊሊ መለሰላት።
“እንግዲያውስ ይህንን ካወቅክ በዚህ መልኩ ነው መንቀሳቀስ የሚገባህ”
ብላ ቫለንቲና ተናገረች እና በማስከተልም “አንተ የድርሻህን ተወጥተሃል ይገባዋል ብለህ ያሰብከውንም ድርድር አቅርበህለታል በዚህ ነገርህ ከተናደደ
ግን በጣም መጥፎ ነገር ነው።”
“በጣም መጥፎ ነው ያልሽው?” ብሎ ዊሊ በድንጋጤ ድምፅ ጮክ ብሎ
ተናግሮ አፉን በእጁ ይዞ ቆየ “በጣም መጥፎ ነው ያልሽው ቫለንቲና? እሱ
እኔ ላይ ሊያደርግ የሚችላቸውን ነገሮች አስበሻቸዋል? በቃ ይገድለኛል።” አላት ቫለንቲናም ረጋ ብላ ጭንቅላቷን ከወንበሩ መደገፊያ ላይ አስደግፋ አይኗን ዘግታ ለጥቂት ጊዜ ዝም አለች፡፡
“አንተ እነዚህን ሜክሲኮያውያንን አታቃቸውም። ከዚህ በፊት ከሮዲሪጉዜ
ጋር በጠፉ ሰዎች ዙሪያ ለወራት ያህል አብረን ስንሰራ እንደነበር ነግሬሃለሁ
አይደል?”
ያ እኮ ያ የማይረባ የበጎ አድራጎት ሥራ ነው” ብሎ ዊሊ ጮኸባት እና
“ይሄ ግን ይለያል!” አላት።
ቫላንቲናም በውስጧ ይህማ አንተ የምታስበው እና ከላይ የሚታየው
ሥራዬ ነው!' አለች፡፡
“ለማንኛውም እውነታው ምን መሰለህ? አንተ እንዳልከው ሁለታችንንም ሊገድለን ይችላል። እመነኝ ይህንን ግን አያደርገውም፡፡ ዊሊ ሎስ አንጀለስ
ላይ አንተ ታስፈልገዋለህ። ማለቴ ከጠቃሚ ሰዎች ጋር ያለህ ግንኙነት እና
ህጋዊ ድርጅቶችህን ሊጠቀምባቸው ይፈልጋል። ይሄውልህ በአንተ እጅ ላይ
ብዙ ጠቃሚ ካርዶች አሉ። ከአንተ የሚጠበቀው ነገር እነዚህን ካርዶች
በአግባቡ መጫወት ብቻ ነው።” አለችው፡፡
ዊሊ አፉን በመክፈት የሆነ ነገር ሊናገር ሲል ቫላንቲንና አቋረጠችው እና
“አሁን ደክሞኛል ውዴ፡፡ ያለፉት ቀናቶችን በጣም ስሠራ ነበር ያሳለፍኩት። በዚህ ጉዳይ ላይ ልታወራኝ ከፈለግክ ግን ራት ላይ ልታነሳው ትችላለህ።” ብላ አይኗን ከድና መደገፊያው ላይ ራሷን አሳረፈች፡፡
“ሮዲሪጌዜ ጋር አሁን ልደውልለት?” አላት ዊሊ በጭንቀት እንደተዋጠ፡፡
ቫለንቲናም አይኗን ሳትከፍት “ስለ ፈጣሪ ብለህ ዊሊ እስቲ አንድ አንዴ እንኳን ወንድ ወንድ ሽተት እንጂ” ብላ ቀዝቀዝ ባለ ስሜት መለሰችለት።
ይህንን የሰማው ሹፌራቸውም ድምፁን አፍኖ እየሳቀ ወደ ፊት መንዳቱን ቀጠለ።
✨ይቀጥላል✨
የመጎናፀፍ ምክንያቶች ቫለንቲና ሳታቋርጥ ስራተኞቿን በመሸለሟ እና
በመቅጣቷ የመጡ ስኬቶች ነበሩ።
የዚህ ሳምንት አሰራር ግን ቅጣትን መሰረት ያደረገ ነበር። ቢሮ ውስጥ
በቆየችባቸው የአንድ ሰአት ጊዜዋ ውስጥ አካውንታንቱ እና ረዳቶቹን ስታሸብር ነበር።
“ሥራዎች በአግባቡ እንዲከናወኑ ከፈለግክ ሥራውን አንተ ራስህ ስራው ብላ ቴሪ ኤንጀልስ የተባለውን የኤል.ኤ ኦፊስ ማናጀርን ወረፈችው።
“የባለፉት ስድስት ወራት ፋይሎች በሙሉ የማይረቡ እና ያልተደራጁ ናቸው። እዚህ በምቆይበት ጊዜ ላይም እኔው ራሴ አደራጃቸዋለሁ።በሚቀጥለው ጊዜ ግን እንደዚህ አይነት ጉዳይ ቢገጥመኝ ቦታህን ትለቃለህ”
የገንዘብ ነክ ጉዳዮች ላይ ያሏትን ሥራዎች ከጨረሰች በኋላ ቢሮው
ውስጥ ያልተገኙ ሠራተኞች ላይ ቅጣቶችን ወስና ከቢሮዋ ወጣች። ሌሎች ልትሠራቸው ያሰበቻቸውን ሥራዎችንም ሎስ አንጀለስ ውስጥ በቆየችባቸው ጊዜያት ላይ በደንብ አጠናቅቃ ወደ ሜክሲኮ ካቦ ተመለሰች። ሎስ አንጀለስ በቆየችባቸው ጊዜያት ላይ እሷን ቫለንቲና ባደንን ማንም ሰው ሊያሞኛት እንደማይችል ተገቢውን ትምህርት ለሁሉም ሰዎች ሰጥታ ወደ ካቦ ስለተመለሰች፤ ቆይታዋ ስኬታማ እንደሆነ ገምታ ጥሩ ስሜት ተሰማት።
ዊሊ ባደን በየጊዜው ወደ እሷ እየደወለ አሁን ላይ አብሮት እየሰራው በሚገኘው ሰው ላይ ያለውን ፍራቻ በመንገር ሲነዘንዛት ብቻ ትንሽ ምቾት አጥታ ነበር፡፡ አሁን ላይ የሚያስፈልጋቸው ነገር ቢኖር ሚድያዎች ስለ ሊዛ ፍላንገን እና ስለ ዊሊ የፍቅር ግንኙነት እንዲሁም ደግሞ ስለዚያች የተረገመች ሳይኮሎጂስት
ዶክተር ሮበርትስ የሚያወሩትን ነገሮች
እንዲያቆሙ ማድረግ ብቻ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ ግን ነገሮች ወደ ቀድሞ ሰላማዊ ሁኔታቸው ይመለሳሉ። .
“እግዚአብሔር ይመስገን እንኳን መጣሽልኝ” አላት ዊሊ ባደን ለቫለንቲና፡፡ ዊሊ ባደን ራሱ አውሮፕላን ማረፊያ ድረስ ሊቀበላት በመምጣቱ ትንሽ ገርሟታል። የታርማክ መኪናቸው ሹፌር የቫለንቲናን ቦርሳዎች ተቀብሏት መኪናው ውስጥ ካስገባ በኋላ መኪናውን መሾፈር ጀመረ።
ይሄኔም ዊሊ ባደን “ሁለት ቀን ሙሉ ስደውልለት እኮ ስልኩን አያነሳም!”
ብሎ ፍርሃት በወረረው ድምፅም “
ሰማሺኝ? ሁለት ቀን ሙሉ ስልክ
አያነሳም፡፡ በጣም ሳይናደድብኝ አልቀረም!” አላት፡፡
“ማን ነው የተናደደው?” ብላ ቫለንቲና ጠየቀችው፡፡
“ስለማን ነው እያወራሁኝ ያለሁት?” ብሎ በንዴት ጠየቃት፡፡
“ሮዲሪጉዜን ነው?” ብላ ቫለንቲና በረዥሙ ተነፈሰች።
“አዎ ሮዲሪጉዜ ነዋ!” ብሎ በፍርሃት ድምፀት ውስጥ ሆኖ “እሱ ጋር
ሥራ መሥራት አልነበረብንም፡፡ ይሄ የማይረባ ድርድር...” ብሎ
“ብዙ የሥራ ዕድልን እና ሀብትን ይዞልን ይመጣል።” ብላ ቫለንቲና እሱ ሊናገር ባላሰበው መልኩ መለሰችለት እና ክንዱን ጭምቅ አድርጋ በመያዝ “ዊሊ መረጋጋት ይኖርብሃል። በዚህ ጊዜ ላይ ፍራቻን ማሳየት የለብህም። እንደ ሮዲሪጉዜ ያሉ ሰዎች የሌሎች ሰዎችን ድክመት ልክ ሻርክ ደምን በሚያሸትበት ሁኔታ ነው የሚያሽቱት። ከእንደ እሱ አይነት ሰዎች ጋር እንዳደግኩኝ ነግሬሀለሁ አይደል? እዚህ ነገሮች በተለየ መልኩ ነው
የሚከወኑት።” አለችው፡፡
“እሱንማ አውቃለው” በማለት ዊሊ መለሰላት።
“እንግዲያውስ ይህንን ካወቅክ በዚህ መልኩ ነው መንቀሳቀስ የሚገባህ”
ብላ ቫለንቲና ተናገረች እና በማስከተልም “አንተ የድርሻህን ተወጥተሃል ይገባዋል ብለህ ያሰብከውንም ድርድር አቅርበህለታል በዚህ ነገርህ ከተናደደ
ግን በጣም መጥፎ ነገር ነው።”
“በጣም መጥፎ ነው ያልሽው?” ብሎ ዊሊ በድንጋጤ ድምፅ ጮክ ብሎ
ተናግሮ አፉን በእጁ ይዞ ቆየ “በጣም መጥፎ ነው ያልሽው ቫለንቲና? እሱ
እኔ ላይ ሊያደርግ የሚችላቸውን ነገሮች አስበሻቸዋል? በቃ ይገድለኛል።” አላት ቫለንቲናም ረጋ ብላ ጭንቅላቷን ከወንበሩ መደገፊያ ላይ አስደግፋ አይኗን ዘግታ ለጥቂት ጊዜ ዝም አለች፡፡
“አንተ እነዚህን ሜክሲኮያውያንን አታቃቸውም። ከዚህ በፊት ከሮዲሪጉዜ
ጋር በጠፉ ሰዎች ዙሪያ ለወራት ያህል አብረን ስንሰራ እንደነበር ነግሬሃለሁ
አይደል?”
ያ እኮ ያ የማይረባ የበጎ አድራጎት ሥራ ነው” ብሎ ዊሊ ጮኸባት እና
“ይሄ ግን ይለያል!” አላት።
ቫላንቲናም በውስጧ ይህማ አንተ የምታስበው እና ከላይ የሚታየው
ሥራዬ ነው!' አለች፡፡
“ለማንኛውም እውነታው ምን መሰለህ? አንተ እንዳልከው ሁለታችንንም ሊገድለን ይችላል። እመነኝ ይህንን ግን አያደርገውም፡፡ ዊሊ ሎስ አንጀለስ
ላይ አንተ ታስፈልገዋለህ። ማለቴ ከጠቃሚ ሰዎች ጋር ያለህ ግንኙነት እና
ህጋዊ ድርጅቶችህን ሊጠቀምባቸው ይፈልጋል። ይሄውልህ በአንተ እጅ ላይ
ብዙ ጠቃሚ ካርዶች አሉ። ከአንተ የሚጠበቀው ነገር እነዚህን ካርዶች
በአግባቡ መጫወት ብቻ ነው።” አለችው፡፡
ዊሊ አፉን በመክፈት የሆነ ነገር ሊናገር ሲል ቫላንቲንና አቋረጠችው እና
“አሁን ደክሞኛል ውዴ፡፡ ያለፉት ቀናቶችን በጣም ስሠራ ነበር ያሳለፍኩት። በዚህ ጉዳይ ላይ ልታወራኝ ከፈለግክ ግን ራት ላይ ልታነሳው ትችላለህ።” ብላ አይኗን ከድና መደገፊያው ላይ ራሷን አሳረፈች፡፡
“ሮዲሪጌዜ ጋር አሁን ልደውልለት?” አላት ዊሊ በጭንቀት እንደተዋጠ፡፡
ቫለንቲናም አይኗን ሳትከፍት “ስለ ፈጣሪ ብለህ ዊሊ እስቲ አንድ አንዴ እንኳን ወንድ ወንድ ሽተት እንጂ” ብላ ቀዝቀዝ ባለ ስሜት መለሰችለት።
ይህንን የሰማው ሹፌራቸውም ድምፁን አፍኖ እየሳቀ ወደ ፊት መንዳቱን ቀጠለ።
✨ይቀጥላል✨
👍4
#ህመምህ አሞኛል
የጥበብን ቀኝ እጅበቀኙ የዘየረ፣
ነብዩ ሰለሞን “ያማል” ይል ነበረ፡፡
ቆሞ ሲጠብቃት ቀርታበት ወዳጁ፣
አንድ እሷ የምትሞላው፣
ኦና ቢሆን ደጁ፣
ግትልትል መኪናው፣
ታክሲው አውቶብሱ፣
የሰው ግሳንግሱ፣
የሰው አጋሰሱ፣
ላይኑ አልሞላ ብሎት፣
ለተራበች ነፍሱ፣
“ያማል” ይል ነበረ፡፡
በአይኖቹ አንቀልባ በእንባ መቀነቻ፣
ተስፋ እንደቋጠረ፣
ማዶ ማዶ እያየ በተሰበረ ቅስም “ያማል”ይል ነበረ!
እኔ መች ተሰማኝ የጓዴ ህመሙ፣
የታባቴ ገብቶኝ የጥበቃ ጥሙ፣
ዛሬ ግን አወቅኩት...ብቻዬን ባወራው እብድ ይሉኛል ብዬ፣
ህመምን ላለፍካት ህመሜን ላኩልህ ʻባረቄʼ ጠቅልዬ፡፡
እየውልህ ጓዴ...
ያች የነገርኩህ ልጅ የፍቅር እትብቴ፣
ለተስፋዬ ደብር ያኖርኳት ፅላቴ፣
በራችንን ዘግተን ሲንቆረቆር ህልሜ ሲንቆረቆር ህልምህትዝ አይልህም ጓዴ፣
እልፍ ʻዝም በልʼ ያልኩህ
(እ.................................................................ሷ!)
የሰው ሁሉ ዳና ʻየሷ ነውʼ እያልኩኝ፣
ከበሬ ሲርቁ ተስፋ እያስወረድኩኝ፣
የጠበቅኳት ፍቅሬ - መቼ ለታ መጣች፣
ጓዴ ሃሌ ሉ.....ያ የኔ ፀሐይ ወጣች፣
ከምዕራብ አድማስ ብርሃኗን ነዛች፡፡
ተዘግቶ የነበር በሬ ተከፈተ፣
ገድሎኝ የነበረው ብቸኝነት ሞተ፡፡
ሊተን የነበረ የመውደዴ ተስፋ፣
ፀጉሬ ጫፍ ላይ ሲደርስ ተመልሶ ፋፋ፡፡
ጥቋቁር ተራሮች ፍቅሬን የጋረዱ፣
የእግሯን ዳና ሰምተው ከፊቴ ተናዱ፡፡
ጓዴ ሃሌሉ.....ያ
አበቦች ደመቁ፣
የመከኑ ምንጮች ኩል ውሃ አፈለቁ፣
በጠራራ ግንቦት አደይ ምድሩን ሞላ፣
ምን ልበልህ ሌላ...ሃሃሃ ሃሃ ሃሃ እኔ እምልህ ጓዴ፣
“የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ እንደመጠበቅ...”ነበረ አይደል ያልከው ?
ከመቅረት የባሰ አመጣጥ እንዳለ አንተ መቸ አወቅከው ?!!
እና የነገርኩህ ልጅ...
መኖሬን ረስታ፣
ደብሬን ክፍቱን ትታ፣
እግዜር የሰማውን የእምነት ቃሏን ክዳ፣
ከበዓድ ተዛምዳከባዕድ ተዋልዳ፣
“አ...ንተ እስካሁን አለህ ?”አትለኝ መሰለህ…ል...ሙትልህ ጓዴ !
እንዲህ ነው ያለችኝ፣
ቁልቁል እያየችኝ፡፡
እንዲህ ናት ቅፅበቷ...
እሷ ከፊቴ አለች፡፡
የጎደፈ እምነቷን፣
በቃል እያጠበች፡፡
ውራጅ ፍቅሯን ገዝቶ፣
ደረቱን የነፋ ʻፈረንጅʼ ጎኗ ቆሟል፣
ከሷና እሱ ኋላ፣
ተራራ ሸንተረር ዛፍ ቅጠሉ ታምሟል..
.ደመናውም ደክሟል...ከደመናው በላይ አፉን በእጁ ይዞ፣
እግዜርም ተደምሟል(ወቸ ጉድ እያለ…)
ፈረንጁ....
እጁን ʻመክሊቴʼ ላይ ጣል አድርጎ ያየኛል፣
ያኔ ያልከው ʻህመምʼ ጎኔን ይወጋኛል፡፡
የምትወዳት ልጅ በሌላ መታቀፍ፣
ከዚህ በላይ ስቃይ ከዚህ በላይ መቅፈፍ...ምናለበት
እሱ...ግዴለም ይቀፋት፣
በፈራረሰ ቤትጭቃው በረገፈ፣
በንፁህ ልቦና በቀን ባልጎደፈ፣
አንዲት አግዳሚ ላይ ጎን ለጎን ተቀምጠን፣
አንድ እርሳስ ተካፍለን አንድ መፅሐፍ ገልጠን፣
የአበበን በሶ - የጫላን ስል ጩቤ፣
እኔ እንጅ የማስታውስ - ልቤ ላይ ከትቤ፣
ፈረንጁ ምን እዳው… ከሀዲን ያስከዳው፡፡
የአየለን ብርታት፣
የጫልቱን እንስራ፣
በቀዳዳው ጣራ፣
ጉንጯ ላይ ያረፈች የምተገርም ጮራ...፡፡
ቆዳዋ ላይ ያሉ ገራገር ስስ ፀጉሮች፣
ጥቁር ሰሌዳ ላይ ተስፋ የሚቃርሙ የልጀነት አይኖች፡፡
አርፈው የማይቆሙ፣
ተወዛዋዥ እግሮች፣
እርሱ መቸ አያቸው...
ከአንጎሉ ጥልቀት በትዝታ መረብ መች አጠመዳቸው፡፡
ምቾት ያደለበው ስጋዋን ይቀፈው፣.
እንደመሲህ ካባ በእምነት የምነካው፣
ሰገባ ቀሚሷን በድፍረት ይግፈፈው…
ከሰማይ የራቁኝ - ጡቶቿ መካከል፣
በእፎይታ ይረፍ-በአርያም ይንሳፈፍ…ልሙትልህ ጓዴ፣
እጎኔ ብትኖርʻእናቷን ጨረቃʼ ያስባለህ ህመምህ፣
በጠራራ ፀሃይ ይነሳብህ ነበር፡፡
እኔ ተነሳብኝ ሾይጧን ወሰወሰኝ፣
እከካም ክህደት የምፎክትበት ጥፍርህን አውሰኝ፡፡
የኔና እሷን ነበር ዛሬ ያላወራው፣
ʻእ ና ቱ ንʼ ...ሸለቆው እ ና ቱ ን ተራራው፡፡
እፊቴ የቆመው... እ ና ቱን ፈረንጁ፣
ወገቧን ያቀፈው እ ና ቱ ን ቀኝ እጁ፡፡
ስማኝማ አንተ ሰው..
.የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ እንደመጠበቅ አልነበረ ያልከው…
ከመቅረት የባሰ አመጣጥ እንዳለ አንተ መች አወቅከው፡፡
አይዞን ወዳጄ፣
ያው እንዳንተ ደጃፍ ኦና ሆኗል ደጄ፣
አሁን ናፍቀኸኛል...
እጠብቅው የለኝ ትጠብቀው የ ለህ፣
እንገናኝና ʻአረቄʼ እየጠጣን፣
ግጥም እንፃፍለት፣
ለድህነታችን ጥበቃን ላሳጣን
!!እናቱን ድህነት !!
እናቱን ጥበቃ
!!በቃ!!
የጥበብን ቀኝ እጅበቀኙ የዘየረ፣
ነብዩ ሰለሞን “ያማል” ይል ነበረ፡፡
ቆሞ ሲጠብቃት ቀርታበት ወዳጁ፣
አንድ እሷ የምትሞላው፣
ኦና ቢሆን ደጁ፣
ግትልትል መኪናው፣
ታክሲው አውቶብሱ፣
የሰው ግሳንግሱ፣
የሰው አጋሰሱ፣
ላይኑ አልሞላ ብሎት፣
ለተራበች ነፍሱ፣
“ያማል” ይል ነበረ፡፡
በአይኖቹ አንቀልባ በእንባ መቀነቻ፣
ተስፋ እንደቋጠረ፣
ማዶ ማዶ እያየ በተሰበረ ቅስም “ያማል”ይል ነበረ!
እኔ መች ተሰማኝ የጓዴ ህመሙ፣
የታባቴ ገብቶኝ የጥበቃ ጥሙ፣
ዛሬ ግን አወቅኩት...ብቻዬን ባወራው እብድ ይሉኛል ብዬ፣
ህመምን ላለፍካት ህመሜን ላኩልህ ʻባረቄʼ ጠቅልዬ፡፡
እየውልህ ጓዴ...
ያች የነገርኩህ ልጅ የፍቅር እትብቴ፣
ለተስፋዬ ደብር ያኖርኳት ፅላቴ፣
በራችንን ዘግተን ሲንቆረቆር ህልሜ ሲንቆረቆር ህልምህትዝ አይልህም ጓዴ፣
እልፍ ʻዝም በልʼ ያልኩህ
(እ.................................................................ሷ!)
የሰው ሁሉ ዳና ʻየሷ ነውʼ እያልኩኝ፣
ከበሬ ሲርቁ ተስፋ እያስወረድኩኝ፣
የጠበቅኳት ፍቅሬ - መቼ ለታ መጣች፣
ጓዴ ሃሌ ሉ.....ያ የኔ ፀሐይ ወጣች፣
ከምዕራብ አድማስ ብርሃኗን ነዛች፡፡
ተዘግቶ የነበር በሬ ተከፈተ፣
ገድሎኝ የነበረው ብቸኝነት ሞተ፡፡
ሊተን የነበረ የመውደዴ ተስፋ፣
ፀጉሬ ጫፍ ላይ ሲደርስ ተመልሶ ፋፋ፡፡
ጥቋቁር ተራሮች ፍቅሬን የጋረዱ፣
የእግሯን ዳና ሰምተው ከፊቴ ተናዱ፡፡
ጓዴ ሃሌሉ.....ያ
አበቦች ደመቁ፣
የመከኑ ምንጮች ኩል ውሃ አፈለቁ፣
በጠራራ ግንቦት አደይ ምድሩን ሞላ፣
ምን ልበልህ ሌላ...ሃሃሃ ሃሃ ሃሃ እኔ እምልህ ጓዴ፣
“የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ እንደመጠበቅ...”ነበረ አይደል ያልከው ?
ከመቅረት የባሰ አመጣጥ እንዳለ አንተ መቸ አወቅከው ?!!
እና የነገርኩህ ልጅ...
መኖሬን ረስታ፣
ደብሬን ክፍቱን ትታ፣
እግዜር የሰማውን የእምነት ቃሏን ክዳ፣
ከበዓድ ተዛምዳከባዕድ ተዋልዳ፣
“አ...ንተ እስካሁን አለህ ?”አትለኝ መሰለህ…ል...ሙትልህ ጓዴ !
እንዲህ ነው ያለችኝ፣
ቁልቁል እያየችኝ፡፡
እንዲህ ናት ቅፅበቷ...
እሷ ከፊቴ አለች፡፡
የጎደፈ እምነቷን፣
በቃል እያጠበች፡፡
ውራጅ ፍቅሯን ገዝቶ፣
ደረቱን የነፋ ʻፈረንጅʼ ጎኗ ቆሟል፣
ከሷና እሱ ኋላ፣
ተራራ ሸንተረር ዛፍ ቅጠሉ ታምሟል..
.ደመናውም ደክሟል...ከደመናው በላይ አፉን በእጁ ይዞ፣
እግዜርም ተደምሟል(ወቸ ጉድ እያለ…)
ፈረንጁ....
እጁን ʻመክሊቴʼ ላይ ጣል አድርጎ ያየኛል፣
ያኔ ያልከው ʻህመምʼ ጎኔን ይወጋኛል፡፡
የምትወዳት ልጅ በሌላ መታቀፍ፣
ከዚህ በላይ ስቃይ ከዚህ በላይ መቅፈፍ...ምናለበት
እሱ...ግዴለም ይቀፋት፣
በፈራረሰ ቤትጭቃው በረገፈ፣
በንፁህ ልቦና በቀን ባልጎደፈ፣
አንዲት አግዳሚ ላይ ጎን ለጎን ተቀምጠን፣
አንድ እርሳስ ተካፍለን አንድ መፅሐፍ ገልጠን፣
የአበበን በሶ - የጫላን ስል ጩቤ፣
እኔ እንጅ የማስታውስ - ልቤ ላይ ከትቤ፣
ፈረንጁ ምን እዳው… ከሀዲን ያስከዳው፡፡
የአየለን ብርታት፣
የጫልቱን እንስራ፣
በቀዳዳው ጣራ፣
ጉንጯ ላይ ያረፈች የምተገርም ጮራ...፡፡
ቆዳዋ ላይ ያሉ ገራገር ስስ ፀጉሮች፣
ጥቁር ሰሌዳ ላይ ተስፋ የሚቃርሙ የልጀነት አይኖች፡፡
አርፈው የማይቆሙ፣
ተወዛዋዥ እግሮች፣
እርሱ መቸ አያቸው...
ከአንጎሉ ጥልቀት በትዝታ መረብ መች አጠመዳቸው፡፡
ምቾት ያደለበው ስጋዋን ይቀፈው፣.
እንደመሲህ ካባ በእምነት የምነካው፣
ሰገባ ቀሚሷን በድፍረት ይግፈፈው…
ከሰማይ የራቁኝ - ጡቶቿ መካከል፣
በእፎይታ ይረፍ-በአርያም ይንሳፈፍ…ልሙትልህ ጓዴ፣
እጎኔ ብትኖርʻእናቷን ጨረቃʼ ያስባለህ ህመምህ፣
በጠራራ ፀሃይ ይነሳብህ ነበር፡፡
እኔ ተነሳብኝ ሾይጧን ወሰወሰኝ፣
እከካም ክህደት የምፎክትበት ጥፍርህን አውሰኝ፡፡
የኔና እሷን ነበር ዛሬ ያላወራው፣
ʻእ ና ቱ ንʼ ...ሸለቆው እ ና ቱ ን ተራራው፡፡
እፊቴ የቆመው... እ ና ቱን ፈረንጁ፣
ወገቧን ያቀፈው እ ና ቱ ን ቀኝ እጁ፡፡
ስማኝማ አንተ ሰው..
.የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ እንደመጠበቅ አልነበረ ያልከው…
ከመቅረት የባሰ አመጣጥ እንዳለ አንተ መች አወቅከው፡፡
አይዞን ወዳጄ፣
ያው እንዳንተ ደጃፍ ኦና ሆኗል ደጄ፣
አሁን ናፍቀኸኛል...
እጠብቅው የለኝ ትጠብቀው የ ለህ፣
እንገናኝና ʻአረቄʼ እየጠጣን፣
ግጥም እንፃፍለት፣
ለድህነታችን ጥበቃን ላሳጣን
!!እናቱን ድህነት !!
እናቱን ጥበቃ
!!በቃ!!
👍1
#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
.....ናትናኤል ጊዜ ሳያጠፋ ታክሲ ተሣፍሮ ወደ ለገሃር ሄደ፡፡ ደጋግሞ ደውሎ ነበር ስልኩ የተነሳለት፡፡ቀደም ብሎ የመሥሪያ ቤቷ ጓደኛዋ ምህረትጋ ደወሎ ርብቃን አቅርቢልኝ ሲላት: እሁንም ወደ ስራ
ገበታዋ አለመመሰሏን ስትነግረው አለቅጥ ተጨነቀ፤ከራሱ ጋር ክርክር
ገጠመ፡፡ እንደታመመችና ቤቷ ደውሎ ከቻለም ሄዶ ቢያያት እንደሚሻል
ምህረት ስትነግረው መንፈሱ ሸፈተበት፡፡ ልቡ ላይ እንደጦር የተሸነቀረበት
ግን ሌላ ነበር
“በጣም አሟታል እንዴ?” አላት ምህረትን ቅንድቦቹን አጠጋግቶ፡፡ “ምንድነው በሽታዋ ማለቴ…”
“እንዴት ነው ነገሩ..ኣላወቅህም ማለት ነው? ወይስ…ናትናኤል ርብቃ'ኮ እርጉዝ ነች፡፡”
ድንገት እንደመሽ ሁሉ ጭልምልም አለበት ፤ ጭንቅላቱ እንደ ድንጋይ ከበደው፤ ማጅራቱን ጨምድዶ ያዘው፡፡ አንድ ቃል ብቻ ይደጋግም ጀመር “ፈጣሪዬ! . ፈጣሪዬ! ፈጣሪዬ! ስልኩን ከዘጋ በኋላ በቆመበት ተገትሮ ቀረ፡፡ እንደህፃን ልጅ ቁጭ ብሎ ማልቀስ ፈለገ፡፡ “ርብቃ ... ርብቃ!” ራሱን መቆጣጠር ተሳነው “ገደል ይግባ!” ሁሉ ነገር ገደል ይግባ!” የሚንቀጠቀጥ እጁን ኪሱ ከቶ ከአንድ ቡና ቤት ገብቶ ተቀመጠ፡፡ ለሰዓታት ከራሱ ጋር ተወራጨ፡፡ በመጨረሻ ከቡና ቤቱ ወጥቶ የህዝብ ስልክ ይፈልግ ጀመር፡፡
ስልኩ ቢጠራም የሚያነሳው ሰው አልነበረም፡፡ በሚንቀጠቀጥ ቀኝ
እጁ የስልኩን እጀታ ጨምድዶ ይዞ ተጠባበቀ:: ርብቃ'ኮ እርጉዝ ነች ስልኩ
ይጠራል፤ የማያነሳ የለም፡፡ ቀጥታ እቤቷ ድረስ ብሄድስ? አሰበ፡፡ መሄድ የለብኝም:: እሷንም ቢሆን ለባሱ አደጋ ማጋለጥ ነው የሚሆነው፡፡ ደጋግሞ ደውሎ ነበር ስልኩ የተነሳለት
“ሀሎ” አለ ስልኩ እንደተነሳ ቀድሞ፡፡ ድምፅ ተጠባበቀ፡፡ ግን ምንም
አልነበረም:: መልሶ “ሃሎ አለ የሚንቀጠቀጥ ድምፁን ማረጋጋት
እየታገለ፡፡
“ናቲ..ናናቲ” ድምጿን ከመቅጽፅት ለየው፡፡ ቢሆንም በጣም የደከመ ድምጽ ነበር፡፡
“ርብቃ! ደህና ነሽ…?”
“ናቲ...ናቲ አቃጠሉኝ..ና…” .
“ናትናኤል ነኝ ርብቃ… ጮክ በይ አይሰማኝም፡: ርብቃ መሥሪያ
ቤትሽ ደውዬ ነበር፡፡ ርብቃ… እ?… አይሰማም፡፡” ድምጿ እየደከመበት ሄደ፡፡
ሌላ ሰው ስልኩን እንደተቀበላት ተረዳ፡፡
“ሀሎ፡፡” አለ ለስለስ ያለ የወንድ ድምፅ፡፡
“ሃሎ.… እባኮት ርብቃን ነበር፡፡”
“ማን ልበል? ” .
“ሀሎ..እባኮት ርብቃን ያቅርቡልኝ::” ናትናኤል ረጋ ብሎ ጠየቀ፡፡
“ይቅርታ፡፡ትንሽ አሟታል፡፡ በስልክ መቅረብ አትችልም::
የምነግርልዎት መልዕክት ካለ.….”
"እሷኑ ለማነጋገር ስለምፈልግ ነበር፡፡” ናትናኤል ጠንከር አለ፡፡
“ይቅርታ… ስትነጋገር ስለሚደክማት ነው፡፡ መልዕክት ካሎት ልንገርሎት፡፡ ታናሽ ወንድሟ ነኝ ብስራት ነኝ፡፡”
ናትናኤል ለማስታወስ ሞከረ፡፡ ቤተሰቦቿን ብዙም አልቀረባቸውም፤ ቢሆንም ከብስራት ጋር ከአንድ ሁለት ሦስት ጊዜ ተገናኝተዋል፡፡ ብስራት ገና ሃያ ዓመት ያልሞላው ወጣት ወንድሟ ነው::
“እንደምንዋልክ ብስራት፡፡ ናትናኤል ነኝ፤
ታስታውሰኛለህ? የርብቃ..እ… ”
“እዎ እዎ አስታውስሃለሁ፡፡ እንደምንድነህ? ደህና ነህ? ምነው
ጠፋህ? ርብቃ በጣም አስባለች፡፡ ለምን ብቅ አትልም? ”
“እ..” ናትናኤል አመነታ፡፡ “ምን መሰለህ ብስራት መምጣት እንኳን አልችልም፡፡ ግን እሷ እንዴት ነች?”
“አሟታል…በጣም ነው የታመመችው ሐኪም ቤት እያመላለስናት ነው::”
“ምን አሉ ሐኪሞቹ? ማለቴ ምንድነው?” ናትናኤል በልቡ የሚንቀዋለለውን ለመጠየቅ ጭንቅ አለው::
“አላወቁላትም፡፡ ግን ምግብ አይበላላትም፤ ስትበላም አይረጋላትም፡፡
ሰውነቷ ላይ ግን ችግር የለባትም፡፡ 'ጭንቀት ነው' ነው የሚሉት ሐኪሞች፡፡
ምን እንደሚያስጨንቃት ግን ሊገባን ኣልቻለም፡፡ በጣም ደክማለች::
ናትናኤል መጥተህ ብታያት ጥሩ ነበር:: በእንቅልፍ ልቧ ሁሉ ስምህን
ትጠራላች፤ ከቀን ወደቀን እየባሰባት ነው፡፡” ናትናኤል በረጅሙ ተነፈሰ፡፡ እጁን ግንባሩ ላይ ጫነ፡፡ ከራሱ ጋር ክርክር ገጠመ:: የፈለገው ይምጣ ሄዶ ያያታል፡፡ መቼም በቤቷ አካባቢ ሊያንዣብቡ ይችሉ ይሆናል፡፡ ግን ምርጫ የለውም:: ሹልክ ብሎ ገብቶ ሹልክ ብሎ ይወጣል ወሰነ::
“ብስራት መደወሌን ለማንም አትናገር ዛሬ ማታ መጥቼ አያታለሁ እሺ? ልክ ከምሽቱ አስራ ሁለት ተኩል ሲሆን ውጭ በሩጋ ጠብቀኝ” ናትናኤል ስልኩን ከዘጋ በኋላ በግራው ያንጠለጠለውን ትንሽ የሽራ
ሻንጣ ይዞ እዚያው ለገሃር ኣቅራቢያ ወዳለ አነስተኛ ቡና ቤት ተመልሶ ገባ፡፡
ጥግ ወዳለ ወንበር ሄዶ ሰውነቱን ለማርገብ፣ ለማረጋጋት በዝምታ
ተቀመጠ፡፡ በግራሶና ዘይት የተጨማለቀ ሰማያዊ ቱታ ለብሷል። ጭንቅላቱ
ላይ ያጠለቀው ዙሪያው እንደጠወለገ ቅጠል የተልፈሰፈሰው ባርኔጣ በግንባሩ
ላይ ኣዝምሞ ፊቱን ሸፍኖታል፡፡ ከደረት ኪሱ ሲጋራ አውጥቶ ከሚንቀጠቀጥ እጁ ጋር እየታገለ ከለኮሳት በኋላ ክብሪቱን እያጠፋ ሲጋራዋን ምጥጥ አደረጋት፡: “ርብቃ... ርብቃ.… ምነው አጠገብሽ መሆን ብችል!”
“ምን ልታዘዝ::” አለችው ሰማያዊ ሽርጥ ወገቧ ላይ ሸብ ያደረጎች አስተናጋጅ የለበሰውን ቆሻሻ ቱታ ስታይ ድምጿን ቆጥብን አድርጋ::
“ቡና፡፡” አላት ቀና ብሎ አያቷት የዋጠውን የሲጋራ ጭስ ቀረጁሙ እየለቀቀ፡፡
“ሂሣብ በቅድሚያ ነው የሚከፈለው፡፡” አለች ሁለት እጆቿን በጎንና ጎን የሽርጥ ክሶች ውስጥ እየወሸቀች፡፡
ከቀኝ ኪሱ ውስጥ ሣንቲሞች አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ በተን እደረገላት፡፡ ሃሳቡ ግን ሌላ ቦታ ነበር፡፡ ርብቃ ለምን ደበቀችው? «ወይስ ወሯ ገና ነው ማለት ነው ሊሆን አይችልም:: ደብቃው ነው፡፡ ግን ለምን.… ለምን?
የሚወደው ገጿ መጥቶ ፊቱ ላይ ድቅን አለበት፡፡ ርብቃ'ኮ እርጉዝ ነች የምህረት ድምፅ እቃጨለበት፤ አሟታል ምግብ አይበላላትም ብትበላም አይረጋላትም “ጭንቀት ነው" ነው የሚሉት ሐኪሞቹ….
የብስራት ድምፅ ደወለበት...
“አምላከኔ ምን ዓይነት ጉድ ወስጥ ነው የከተትከኝ ኣለ እምላከ ከፊት ለፊቱ ባለ ወንበር ላይ የተቀመጠ ይመስል ፊት ለፊት አፍጥጦ፡፡
ምንድነው ሊያደርግ የሚችለው? ቀጥ ብሎ ፖሊስጋ ሄዶ እጁን መስጠት፡፡ ቢገሉትስ? ይግደሉት፡፡ ከዚህ በላይ ስቃይ መሸከም አይችልም ግን ለፖሊሶችስ ምን ሆንኩ ብሎ እጁን ይሰጣል? ሁሉን ነዋ!.. የሆነውን
ሁሉ ዘርዝሮ ማውጣት ነዋ! ግን ማን ያዳምጠዋል? ማን ያምነዋል? ፍጹም!
ፖሊስ ወጥመድ ነው! እጁን መስጠት ማለት ሞቱን ማፋጠን ማለት ነው፡፡
ለማን ይበጃል መሞቱ? ለርብቃ? ስልጁ? የአብርሃም መሞት ማንን ጠቀመ?
መረጋጋት ነው ያለበት፡፡ ካሁን ወዲያ ወደኋላ ማለት አይችልም፤ መረጋጋት
ነው ያለበት፡፡
ከቁጥጥር ውጭ በሚንቀጠቀጥ ቀኝ እጁ የያዛትን ያለቀች ሲጋራ ለመጨረሻ ጊዜ መጠጣትና ከፊት ለፊቱ ጠረጴዛ ላደ በተቀመጠው የሲጋራ መተርኮሻ ውስጥ ደፈጠጣት፡፡ መረጋጋት…. መረጋጋት ነው ያለበት...
የቡና ቤቱ አስተናጋጅ ያዘዛትን ቡና አምጥታ እፊቱ ደነቀረችለት::
አንስቶ ፉት ኣላው፡፡ ስኳር አልነበረውም:: ክፉኛ መረረው፡፡ ቢሆንም ስኳር
አልጠየቃትም፡፡ ድጋሚ ፉት ኣለው፡፡ ትኩስ ቡና በጉሮሮው አልፎ በሆዱ
ሲተራመስ ስንዝር በስንዝር ተከታትለው:: ሆዱ ጩርርርር ሲል ተሰማው:: ትላንት ምሳ የበላ ነው፡፡ ቢሆንም ምግብ አላሰኘውም:: ከቡናው ድጋሚ ፉት አለለት፡፡ ሰውነቱን ማዝናናት አለበት፤ ማረጋጋት አለበት፡፡በተቀመጠበት ወንበር ላይ በደኋላ ጋለል ብሎ ዓያኖቹን ጨፈናቸው፡፡ ቀኝ እጁ ከደረት ኪሱ ገብቶ ሲጋራና ክብሪት ይዞ ተመለሰ፡፡ ርብቃ ለምን ደበቀችው? በቃ በቃ... ስለርብቃ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
.....ናትናኤል ጊዜ ሳያጠፋ ታክሲ ተሣፍሮ ወደ ለገሃር ሄደ፡፡ ደጋግሞ ደውሎ ነበር ስልኩ የተነሳለት፡፡ቀደም ብሎ የመሥሪያ ቤቷ ጓደኛዋ ምህረትጋ ደወሎ ርብቃን አቅርቢልኝ ሲላት: እሁንም ወደ ስራ
ገበታዋ አለመመሰሏን ስትነግረው አለቅጥ ተጨነቀ፤ከራሱ ጋር ክርክር
ገጠመ፡፡ እንደታመመችና ቤቷ ደውሎ ከቻለም ሄዶ ቢያያት እንደሚሻል
ምህረት ስትነግረው መንፈሱ ሸፈተበት፡፡ ልቡ ላይ እንደጦር የተሸነቀረበት
ግን ሌላ ነበር
“በጣም አሟታል እንዴ?” አላት ምህረትን ቅንድቦቹን አጠጋግቶ፡፡ “ምንድነው በሽታዋ ማለቴ…”
“እንዴት ነው ነገሩ..ኣላወቅህም ማለት ነው? ወይስ…ናትናኤል ርብቃ'ኮ እርጉዝ ነች፡፡”
ድንገት እንደመሽ ሁሉ ጭልምልም አለበት ፤ ጭንቅላቱ እንደ ድንጋይ ከበደው፤ ማጅራቱን ጨምድዶ ያዘው፡፡ አንድ ቃል ብቻ ይደጋግም ጀመር “ፈጣሪዬ! . ፈጣሪዬ! ፈጣሪዬ! ስልኩን ከዘጋ በኋላ በቆመበት ተገትሮ ቀረ፡፡ እንደህፃን ልጅ ቁጭ ብሎ ማልቀስ ፈለገ፡፡ “ርብቃ ... ርብቃ!” ራሱን መቆጣጠር ተሳነው “ገደል ይግባ!” ሁሉ ነገር ገደል ይግባ!” የሚንቀጠቀጥ እጁን ኪሱ ከቶ ከአንድ ቡና ቤት ገብቶ ተቀመጠ፡፡ ለሰዓታት ከራሱ ጋር ተወራጨ፡፡ በመጨረሻ ከቡና ቤቱ ወጥቶ የህዝብ ስልክ ይፈልግ ጀመር፡፡
ስልኩ ቢጠራም የሚያነሳው ሰው አልነበረም፡፡ በሚንቀጠቀጥ ቀኝ
እጁ የስልኩን እጀታ ጨምድዶ ይዞ ተጠባበቀ:: ርብቃ'ኮ እርጉዝ ነች ስልኩ
ይጠራል፤ የማያነሳ የለም፡፡ ቀጥታ እቤቷ ድረስ ብሄድስ? አሰበ፡፡ መሄድ የለብኝም:: እሷንም ቢሆን ለባሱ አደጋ ማጋለጥ ነው የሚሆነው፡፡ ደጋግሞ ደውሎ ነበር ስልኩ የተነሳለት
“ሀሎ” አለ ስልኩ እንደተነሳ ቀድሞ፡፡ ድምፅ ተጠባበቀ፡፡ ግን ምንም
አልነበረም:: መልሶ “ሃሎ አለ የሚንቀጠቀጥ ድምፁን ማረጋጋት
እየታገለ፡፡
“ናቲ..ናናቲ” ድምጿን ከመቅጽፅት ለየው፡፡ ቢሆንም በጣም የደከመ ድምጽ ነበር፡፡
“ርብቃ! ደህና ነሽ…?”
“ናቲ...ናቲ አቃጠሉኝ..ና…” .
“ናትናኤል ነኝ ርብቃ… ጮክ በይ አይሰማኝም፡: ርብቃ መሥሪያ
ቤትሽ ደውዬ ነበር፡፡ ርብቃ… እ?… አይሰማም፡፡” ድምጿ እየደከመበት ሄደ፡፡
ሌላ ሰው ስልኩን እንደተቀበላት ተረዳ፡፡
“ሀሎ፡፡” አለ ለስለስ ያለ የወንድ ድምፅ፡፡
“ሃሎ.… እባኮት ርብቃን ነበር፡፡”
“ማን ልበል? ” .
“ሀሎ..እባኮት ርብቃን ያቅርቡልኝ::” ናትናኤል ረጋ ብሎ ጠየቀ፡፡
“ይቅርታ፡፡ትንሽ አሟታል፡፡ በስልክ መቅረብ አትችልም::
የምነግርልዎት መልዕክት ካለ.….”
"እሷኑ ለማነጋገር ስለምፈልግ ነበር፡፡” ናትናኤል ጠንከር አለ፡፡
“ይቅርታ… ስትነጋገር ስለሚደክማት ነው፡፡ መልዕክት ካሎት ልንገርሎት፡፡ ታናሽ ወንድሟ ነኝ ብስራት ነኝ፡፡”
ናትናኤል ለማስታወስ ሞከረ፡፡ ቤተሰቦቿን ብዙም አልቀረባቸውም፤ ቢሆንም ከብስራት ጋር ከአንድ ሁለት ሦስት ጊዜ ተገናኝተዋል፡፡ ብስራት ገና ሃያ ዓመት ያልሞላው ወጣት ወንድሟ ነው::
“እንደምንዋልክ ብስራት፡፡ ናትናኤል ነኝ፤
ታስታውሰኛለህ? የርብቃ..እ… ”
“እዎ እዎ አስታውስሃለሁ፡፡ እንደምንድነህ? ደህና ነህ? ምነው
ጠፋህ? ርብቃ በጣም አስባለች፡፡ ለምን ብቅ አትልም? ”
“እ..” ናትናኤል አመነታ፡፡ “ምን መሰለህ ብስራት መምጣት እንኳን አልችልም፡፡ ግን እሷ እንዴት ነች?”
“አሟታል…በጣም ነው የታመመችው ሐኪም ቤት እያመላለስናት ነው::”
“ምን አሉ ሐኪሞቹ? ማለቴ ምንድነው?” ናትናኤል በልቡ የሚንቀዋለለውን ለመጠየቅ ጭንቅ አለው::
“አላወቁላትም፡፡ ግን ምግብ አይበላላትም፤ ስትበላም አይረጋላትም፡፡
ሰውነቷ ላይ ግን ችግር የለባትም፡፡ 'ጭንቀት ነው' ነው የሚሉት ሐኪሞች፡፡
ምን እንደሚያስጨንቃት ግን ሊገባን ኣልቻለም፡፡ በጣም ደክማለች::
ናትናኤል መጥተህ ብታያት ጥሩ ነበር:: በእንቅልፍ ልቧ ሁሉ ስምህን
ትጠራላች፤ ከቀን ወደቀን እየባሰባት ነው፡፡” ናትናኤል በረጅሙ ተነፈሰ፡፡ እጁን ግንባሩ ላይ ጫነ፡፡ ከራሱ ጋር ክርክር ገጠመ:: የፈለገው ይምጣ ሄዶ ያያታል፡፡ መቼም በቤቷ አካባቢ ሊያንዣብቡ ይችሉ ይሆናል፡፡ ግን ምርጫ የለውም:: ሹልክ ብሎ ገብቶ ሹልክ ብሎ ይወጣል ወሰነ::
“ብስራት መደወሌን ለማንም አትናገር ዛሬ ማታ መጥቼ አያታለሁ እሺ? ልክ ከምሽቱ አስራ ሁለት ተኩል ሲሆን ውጭ በሩጋ ጠብቀኝ” ናትናኤል ስልኩን ከዘጋ በኋላ በግራው ያንጠለጠለውን ትንሽ የሽራ
ሻንጣ ይዞ እዚያው ለገሃር ኣቅራቢያ ወዳለ አነስተኛ ቡና ቤት ተመልሶ ገባ፡፡
ጥግ ወዳለ ወንበር ሄዶ ሰውነቱን ለማርገብ፣ ለማረጋጋት በዝምታ
ተቀመጠ፡፡ በግራሶና ዘይት የተጨማለቀ ሰማያዊ ቱታ ለብሷል። ጭንቅላቱ
ላይ ያጠለቀው ዙሪያው እንደጠወለገ ቅጠል የተልፈሰፈሰው ባርኔጣ በግንባሩ
ላይ ኣዝምሞ ፊቱን ሸፍኖታል፡፡ ከደረት ኪሱ ሲጋራ አውጥቶ ከሚንቀጠቀጥ እጁ ጋር እየታገለ ከለኮሳት በኋላ ክብሪቱን እያጠፋ ሲጋራዋን ምጥጥ አደረጋት፡: “ርብቃ... ርብቃ.… ምነው አጠገብሽ መሆን ብችል!”
“ምን ልታዘዝ::” አለችው ሰማያዊ ሽርጥ ወገቧ ላይ ሸብ ያደረጎች አስተናጋጅ የለበሰውን ቆሻሻ ቱታ ስታይ ድምጿን ቆጥብን አድርጋ::
“ቡና፡፡” አላት ቀና ብሎ አያቷት የዋጠውን የሲጋራ ጭስ ቀረጁሙ እየለቀቀ፡፡
“ሂሣብ በቅድሚያ ነው የሚከፈለው፡፡” አለች ሁለት እጆቿን በጎንና ጎን የሽርጥ ክሶች ውስጥ እየወሸቀች፡፡
ከቀኝ ኪሱ ውስጥ ሣንቲሞች አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ በተን እደረገላት፡፡ ሃሳቡ ግን ሌላ ቦታ ነበር፡፡ ርብቃ ለምን ደበቀችው? «ወይስ ወሯ ገና ነው ማለት ነው ሊሆን አይችልም:: ደብቃው ነው፡፡ ግን ለምን.… ለምን?
የሚወደው ገጿ መጥቶ ፊቱ ላይ ድቅን አለበት፡፡ ርብቃ'ኮ እርጉዝ ነች የምህረት ድምፅ እቃጨለበት፤ አሟታል ምግብ አይበላላትም ብትበላም አይረጋላትም “ጭንቀት ነው" ነው የሚሉት ሐኪሞቹ….
የብስራት ድምፅ ደወለበት...
“አምላከኔ ምን ዓይነት ጉድ ወስጥ ነው የከተትከኝ ኣለ እምላከ ከፊት ለፊቱ ባለ ወንበር ላይ የተቀመጠ ይመስል ፊት ለፊት አፍጥጦ፡፡
ምንድነው ሊያደርግ የሚችለው? ቀጥ ብሎ ፖሊስጋ ሄዶ እጁን መስጠት፡፡ ቢገሉትስ? ይግደሉት፡፡ ከዚህ በላይ ስቃይ መሸከም አይችልም ግን ለፖሊሶችስ ምን ሆንኩ ብሎ እጁን ይሰጣል? ሁሉን ነዋ!.. የሆነውን
ሁሉ ዘርዝሮ ማውጣት ነዋ! ግን ማን ያዳምጠዋል? ማን ያምነዋል? ፍጹም!
ፖሊስ ወጥመድ ነው! እጁን መስጠት ማለት ሞቱን ማፋጠን ማለት ነው፡፡
ለማን ይበጃል መሞቱ? ለርብቃ? ስልጁ? የአብርሃም መሞት ማንን ጠቀመ?
መረጋጋት ነው ያለበት፡፡ ካሁን ወዲያ ወደኋላ ማለት አይችልም፤ መረጋጋት
ነው ያለበት፡፡
ከቁጥጥር ውጭ በሚንቀጠቀጥ ቀኝ እጁ የያዛትን ያለቀች ሲጋራ ለመጨረሻ ጊዜ መጠጣትና ከፊት ለፊቱ ጠረጴዛ ላደ በተቀመጠው የሲጋራ መተርኮሻ ውስጥ ደፈጠጣት፡፡ መረጋጋት…. መረጋጋት ነው ያለበት...
የቡና ቤቱ አስተናጋጅ ያዘዛትን ቡና አምጥታ እፊቱ ደነቀረችለት::
አንስቶ ፉት ኣላው፡፡ ስኳር አልነበረውም:: ክፉኛ መረረው፡፡ ቢሆንም ስኳር
አልጠየቃትም፡፡ ድጋሚ ፉት ኣለው፡፡ ትኩስ ቡና በጉሮሮው አልፎ በሆዱ
ሲተራመስ ስንዝር በስንዝር ተከታትለው:: ሆዱ ጩርርርር ሲል ተሰማው:: ትላንት ምሳ የበላ ነው፡፡ ቢሆንም ምግብ አላሰኘውም:: ከቡናው ድጋሚ ፉት አለለት፡፡ ሰውነቱን ማዝናናት አለበት፤ ማረጋጋት አለበት፡፡በተቀመጠበት ወንበር ላይ በደኋላ ጋለል ብሎ ዓያኖቹን ጨፈናቸው፡፡ ቀኝ እጁ ከደረት ኪሱ ገብቶ ሲጋራና ክብሪት ይዞ ተመለሰ፡፡ ርብቃ ለምን ደበቀችው? በቃ በቃ... ስለርብቃ
👍2
ማስብ የለበትም:: አለበለዚያ ያብዳል!
አለበለዚያ አእምሮወን ይስታል፡፡
አእምሮውን ወደኋላ አጠንጥኖ የደረሰበትን ያጋጠመውን ድጋሚ መረመረው...
ከትላንት ወዲያ ማታ ዓይኑ ስር ከተፈጸመው ግድያ በኋላ
ሰውነቱን አረጋግቶ መቆየት አልቻለም:: አንዱ እንደቆሰለች ሚዳቆ ቅጠል
በተንኮሻኮሸና ወፍ በረረች ቁጥር መበርገግ ብቻ ሆነ::
“ሩጥ!” ስትለው አሁንም ጥርት ብሎ ይሰማዋል፡፡ “ሩጥ!” እንዴት እንደ ሮጠ ትዝ አይለውም፡፡ ወደ ዋናው የመኪና መንገድ ከገባም በኋላ ሩጫውን አልገታም ነበር፡፡ በመጨረሻ ፍርሃቱ ታግሶለት ሳይሆን ልቡ ልፍረስ ሲለው… አፉ ደም ደም ሲሰው ፥ ድካም ጎሮሮውን ይዞ ሊፈጠርቀው ሲጀምር! ጥጋት ይዞ ቆመና ቁና ቁና እየተነፈሰ አይኖቹን በጨለማው ውስጥ በመጣበት አቅጣጫ አፈጠጣቸው::
ሊያፍነው ቢሞክርም ከሚጨስ ሳንባው እየተጣደፈ በአፍ በአፍንጫው የሚሽቀዳደም የገዛ ትንፋሹ ድምፅ አስጋው፡፡ ከወዲያ ማዶ ትንፋሹን ሰምተው እንዳይመጡ የፈራ ይመስል እጁን አፉ ላይ ጭኖ ቆመ፡፡
ድምፅ የለም፡፡ ዘግይቶ ነበር እርቆ መሄዱንና ዙሪያውም ማንም እንደሌለ የተረዳው ነፍሱ መለስ ያለችለት፡፡ ሲፈራ ሲቸር ከተደበቀበት ጥጋት እየተገላመጠ ወጥቶ በመኪና መንገዱ ጥግ ጥግ እየተራመደ ራቅ ብለው ወደሚታዩ የመሸታ ቤቶች ኣመራ፡፡ በዚያ ሰዓት ርቆ ለመሄድ መሞከር እንዴሌለበት ተረድቷል፡፡ እዚሁ አፍንጫቸው ስር ነው መደበቅ ያለብኝ ብሎ አሰበ፡፡ እይጠረጥሩኝም። እዚሁ ይቆያል ብለው አይገምቱም፡፡አለበለዚያ ርቄ ለመሄድ ከሞከርኩ ወዲህ ወዲያ ስል ያገኙኛል፡፡ ቶሎ አንድ ቦታ ይዤ መርጋት አለብኝ! እመሃላቸው ቢሆንም ማድፈጥ መቻል
አለብኝ፡፡
ትዝ ይለዋል… “እባክሽ የእኔ እህት አልጋ አለ? ” አላት ወደ አንድ አነስተኛ ሆቴል ገባ ብሎ፡፡
ሴትየዋ መልስ ሳትሰጠው አይኖቿን ኣፍ፡ጥጣ መላ ሰውነቱን ትመለከተው ጀመር፡ ጎንበስ ብሎ የገዛ ሰውነቱን ሲመለከት በረገገ፡፡ ከፊት ለፊት ነጭ ሸሚዙ እጆቹ፣ . ክንዱ ሁሉ በደም ተበክሏል፡፡ ለራሱ
እስኪያስደነግጠው ድረስ ክፉኛ በደም ተጨማልቋል፡፡
እ.. ሰዎች ተደባድበው ስገላግል ነው:: እ…አልጋ አላችሁ?”
መልስ ሳትሰጠው ጭንቅላቷን ብቻ ነቀነቀችበት:: ፊቷ ላይ የሚንቀዋለሰውን ያልተቆነጠጠ ፍርሃት ሲመለከት ተስፋ ቆረጠ.. ሌሊቱን ቆሞ ሲያድር አልጋ እንደማታከራየው ገባው:: ለእርዳታ ሳትጮኽ ኡ! ኡ! ብላ ሳታስይዘው ቶሎ ብሎ ወጣና በፍጥነት በጨለማው ውስጥ ተሰወረ::
ድጋሚ ሌላ ሆቴል ከመግባቱ በፊት የኮቱን ቁልፍ ግጥም አድርጎ
ቆልፎ፣ ኮሌታውን ቀልብሶ እጆቹን ከሱሪው ኪስ ውስጥ ወሽቃቸው:: ወደ
ሆቴሉ ሲገባ የፊተኛው አዳራሽ ባዶ ነበር፡፡ ደንበኞች ወጥተው የአዳራሹን
መስኮቶች የምትዘጋጋ አስተናጋጅ ተመለከተ፡፡ፈገግታ አስቀደመና ኣልጋ
ጠየቃት::
“ስድስት ብር፡፡” አለች ስታየው ኮስተርተር ብላ መስኮቶቹን መዘጋጋቷን ሳታቋርጥ፡፡
በደም የተጨማለቁ እጆቹን ከሱሪው - ኪስ ውስጥ እንዴት እንደሚያወጣ ግራ ተጋባ፡፡ በአዳራሹ ውስጥ ያለው ብርሃን ደብዛዛ ቢሆንም እጆቹ የተነከሩበትን ደም ሳትመለከት ልጅቱ የሚሰማት ስሜት አልጋ እንደሚያስከለክለው እርግጠኛ ነበር፡፡
“መጀመሪያ ክፍሉን ልየዋ፡፡” አላት በተቻለው ራሱን ለመግዛት
እየጣረ::
'ተከተለኝ ለማለት ጭንቅላቷን መታ አደረገችና ፊቷን መልሳ ወደ ጓዳ ገባች፡፡ ተከተላት:: ከሚከራየት ክፍል ሲደርሱ በሩን ከፍታ፣ መብራቱን አብርታ ፈቀቅ አለችለት፡፡ ወደ ክፍሉ ገባና ቀልጠፍ ብሎ መብራቱን አጠፋው:: ወዲያው የገንዘብ ቦርሳውን አውጥቶ ከመተላለፊያው በሚመጣው ስስ ብርሃን የአስር ብር ኖት አውጥቶ ሰጣት፡፡
“መልሱን ያዥው እ… መታጠቢያ ቤት ይኖራል?”
ያው!” አለች ከአስር ብሩ የሚመላሶው አራት ብር የእርሷ መሆኑን ስታውቅ ፈገግ ብላ፡፡
መታጠቢያ ቤት ገብቶ በደም የተበከላ ልብሱንና ሰውነቱን አጣጥቦ ወደተከራየ ክፍል ተመለሰ፡፡ አልጋው ላይ በጀርባው ተንጋሎ አይኖቹን ከደነ፡፡ እንቅልፍ ግን አልጎበኘውም፡፡ ሰውነቱ ሊረጋጋለት አልቻለም፡፡
ምንድነው ነገሩ የተዘበራረቀበትን ሁኔታ ትርጉም ሊሰጠው ተጣጣረ:: ሴትዮዋ ከየት መጣች? ሰካራሟ ማነች? ያለጥርጥር የካልቨርትን አድራሻ ትፈልጋለች፡፡ ለዚህም ነው የምሥራችን የገደለቻት:: ግን እሱን ለምን ተወችው? ሠውነቱው በቻ ሳይሆን ሕይወቱን ለማትረፍ የሌላ ስው ሕይወት ለምን አጠፋች? እሷ ማነች? በአውሬው ውስጥ ለውስጥ አለመግባባትና መከፋፈል አለ ማለት ነው? አንደኛው ወገን ሊያጠፋው
ሲፈልግ የተቀረው ወገን ሞቱን አይሻም ማለት ነው? ግን ለምን? የእርሱ
መኖር ማንን ይጠቅማል? እንዴት? የምሥራች መሞትስ ምን ይጨምራል?
ሴትየዋ ማነች? ሰውየውስ? ሰውየው በምሥራች ሞት ለምን ተደናገጠ?
እርሱንስ ለምን ሊገለው ሞከረ? ሴትየዋ ከጀርባው ባትቀድመው ጨርሶት
ነበር'ኮ!”
የምሥራችን ሳይሆን የእርሱን መጥፋትና መሞት የሚሻ ወገን አሉ ማለት ነወ፡፡ ያለ ጥርጥር ይህኛው ወገን ነው ከብርሃምን የገደለው:: ግን እነማን ናቸው? ምንድነው የሚፈልጉት? ግልፅ ነው:: ሁሉም የሚፈልጉት ካልቨርትን ነው፡፡ የካልቨርትን አድራሻ የምታውቅ የምሥራች ብቻ ነበረች፡፡ ሊያስፈራራት ቢላውን ሲያወጣባት ምንድን ነበር ያላችው የምሥራች?'
“አትነካኝም! ጫፌን ብትነካኝ ዮሴፍ ምን እንደሚያደርግ ታውቃላችሁ! ያወጣዋል ምሥጢራችሁን ያውጣዋል! "
አዎ…እንደጠረጠረው ካልቨርት ይዞት የተሸሸገው ምሥጢር ኣለ፡፡አውሬው የምሥጢሩን መጠበቅ ለማረጋገጥ ሲል ካልቨርትን እጁ ማስገባት ቢፈልግም የምሥራችን ለመተናኮል ያልደፈረው ካልቨርት ምሥጢሩን በይፋ ለማውጣት እንዳይሰቀለው በመፍራት መሆን አለበት፡፡ አወሬው የካልቨርት አባራሪ ይምሰል እንጅ እስረኛውም ነው፡፡ ምክንያቱም ካልቨርት የአውሬውን ምሥጢር በመዳፉ አድርጓል፡፡ የአብርሃም አደራ ታወሰው
«ካልቨርትን አግኝ... ካልቨርትን» አብርሃም ትክክል ነው፡፡ ቁልፉ ያለው
ከዚያ ነው፡፡ ካልቨርት የያዘውን ምሥጢር በጁ ያገባ ሁሉ የአውሬኑን እፍንጫ መሰነግ ይችላል፡፡ ግን ምንድነው ምሥጢሩ? የት ነው ካልቨርት...?
የምሥራች ነበረች ኣድራሻውን የምታውቅ፡፡ ሞታለች፡፡ ሌላ ማን አለ? እርሱ ራሱ ! ነግራዋለች፡፡ አዎ… የካልቨርትን ኣድራሻ ነግራዋለች፡፡ እሱ ብቻ ነው የካልቨርትን አድራሻ የሚያውቅ
“እ…እማዬጋ..ድራዳዋ::"
እማዬጋ... ድሬዳዋ.. የት ናቸው እማዬ? እናቷ? ድሬዳዋ ድሬዳዋ የት?
ናትናኤል በተከራየው የሆቴል ክፍል ወስጥ በጀርባወ አልጋው ላይ እንደተንጋለሉ ዓይኖቹን ኮርኒሱ ላይ ተክሎ ቀረ፡፡
በድሬዳዋ እየተዘዋወረ “የምሥራች እናት እያለ አይፈልግ! ስማቸውን እንኳን አያውቅም፡፡ የምሥራች ይልማ:: እርግጥ የምሥራችን አባት ስም ያውቃል አቶ ይልማ... አስር አለቃ ይልማ ቄስ ይልማ
ፈጣሪ ይወቅ! አባቷን ካገኘ ግን እናቷን አገኘ ማለት ነው:: አብረው አይኖሩ
እንደሆንስ? ቢሆንም የእናቷን አድራሻ ሳያውቁ አይቀሩም ግን አባቷንስ ቢሆን “አቶ ይልማ” እያለ በድሬዳዋ ከተማ ቢዞር አባቷን እንዴት ማግኘት ይችላል? የአባታቸውን ስም ቢያውቅ ጥሩ ነበር፡፡ ያንን እንኳን ማግኘት ይችላል፡፡ እ… ተመልሶ ወደ ሆቴሏ ሄዶ የንግድ ፈቃዷ ላይ ማንበብ ይችላል፡፡ የአባቷና የአያቷ ስም ይኖራል፡፡ ግን ከአሁን ወዲያ ወደዚያ
አቅሪቢያ መሄድ በገዛ እጁ መንጠልጠል ነው:: ሰው ቢልክስ? ማንን?
አንዱን የሠፈር ስራፈት ጎረምሳ አምስት ብር ቢያሳየው ሄዶ ያነብለታል
በዚህ ከደገኛ ሰዓት የላከው ወጣት የንግድ ፈቃዷን ተጠግቶ ፊደል ሲቆጥር
“ምንድነው የምትሰራው?” ብለው
አለበለዚያ አእምሮወን ይስታል፡፡
አእምሮውን ወደኋላ አጠንጥኖ የደረሰበትን ያጋጠመውን ድጋሚ መረመረው...
ከትላንት ወዲያ ማታ ዓይኑ ስር ከተፈጸመው ግድያ በኋላ
ሰውነቱን አረጋግቶ መቆየት አልቻለም:: አንዱ እንደቆሰለች ሚዳቆ ቅጠል
በተንኮሻኮሸና ወፍ በረረች ቁጥር መበርገግ ብቻ ሆነ::
“ሩጥ!” ስትለው አሁንም ጥርት ብሎ ይሰማዋል፡፡ “ሩጥ!” እንዴት እንደ ሮጠ ትዝ አይለውም፡፡ ወደ ዋናው የመኪና መንገድ ከገባም በኋላ ሩጫውን አልገታም ነበር፡፡ በመጨረሻ ፍርሃቱ ታግሶለት ሳይሆን ልቡ ልፍረስ ሲለው… አፉ ደም ደም ሲሰው ፥ ድካም ጎሮሮውን ይዞ ሊፈጠርቀው ሲጀምር! ጥጋት ይዞ ቆመና ቁና ቁና እየተነፈሰ አይኖቹን በጨለማው ውስጥ በመጣበት አቅጣጫ አፈጠጣቸው::
ሊያፍነው ቢሞክርም ከሚጨስ ሳንባው እየተጣደፈ በአፍ በአፍንጫው የሚሽቀዳደም የገዛ ትንፋሹ ድምፅ አስጋው፡፡ ከወዲያ ማዶ ትንፋሹን ሰምተው እንዳይመጡ የፈራ ይመስል እጁን አፉ ላይ ጭኖ ቆመ፡፡
ድምፅ የለም፡፡ ዘግይቶ ነበር እርቆ መሄዱንና ዙሪያውም ማንም እንደሌለ የተረዳው ነፍሱ መለስ ያለችለት፡፡ ሲፈራ ሲቸር ከተደበቀበት ጥጋት እየተገላመጠ ወጥቶ በመኪና መንገዱ ጥግ ጥግ እየተራመደ ራቅ ብለው ወደሚታዩ የመሸታ ቤቶች ኣመራ፡፡ በዚያ ሰዓት ርቆ ለመሄድ መሞከር እንዴሌለበት ተረድቷል፡፡ እዚሁ አፍንጫቸው ስር ነው መደበቅ ያለብኝ ብሎ አሰበ፡፡ እይጠረጥሩኝም። እዚሁ ይቆያል ብለው አይገምቱም፡፡አለበለዚያ ርቄ ለመሄድ ከሞከርኩ ወዲህ ወዲያ ስል ያገኙኛል፡፡ ቶሎ አንድ ቦታ ይዤ መርጋት አለብኝ! እመሃላቸው ቢሆንም ማድፈጥ መቻል
አለብኝ፡፡
ትዝ ይለዋል… “እባክሽ የእኔ እህት አልጋ አለ? ” አላት ወደ አንድ አነስተኛ ሆቴል ገባ ብሎ፡፡
ሴትየዋ መልስ ሳትሰጠው አይኖቿን ኣፍ፡ጥጣ መላ ሰውነቱን ትመለከተው ጀመር፡ ጎንበስ ብሎ የገዛ ሰውነቱን ሲመለከት በረገገ፡፡ ከፊት ለፊት ነጭ ሸሚዙ እጆቹ፣ . ክንዱ ሁሉ በደም ተበክሏል፡፡ ለራሱ
እስኪያስደነግጠው ድረስ ክፉኛ በደም ተጨማልቋል፡፡
እ.. ሰዎች ተደባድበው ስገላግል ነው:: እ…አልጋ አላችሁ?”
መልስ ሳትሰጠው ጭንቅላቷን ብቻ ነቀነቀችበት:: ፊቷ ላይ የሚንቀዋለሰውን ያልተቆነጠጠ ፍርሃት ሲመለከት ተስፋ ቆረጠ.. ሌሊቱን ቆሞ ሲያድር አልጋ እንደማታከራየው ገባው:: ለእርዳታ ሳትጮኽ ኡ! ኡ! ብላ ሳታስይዘው ቶሎ ብሎ ወጣና በፍጥነት በጨለማው ውስጥ ተሰወረ::
ድጋሚ ሌላ ሆቴል ከመግባቱ በፊት የኮቱን ቁልፍ ግጥም አድርጎ
ቆልፎ፣ ኮሌታውን ቀልብሶ እጆቹን ከሱሪው ኪስ ውስጥ ወሽቃቸው:: ወደ
ሆቴሉ ሲገባ የፊተኛው አዳራሽ ባዶ ነበር፡፡ ደንበኞች ወጥተው የአዳራሹን
መስኮቶች የምትዘጋጋ አስተናጋጅ ተመለከተ፡፡ፈገግታ አስቀደመና ኣልጋ
ጠየቃት::
“ስድስት ብር፡፡” አለች ስታየው ኮስተርተር ብላ መስኮቶቹን መዘጋጋቷን ሳታቋርጥ፡፡
በደም የተጨማለቁ እጆቹን ከሱሪው - ኪስ ውስጥ እንዴት እንደሚያወጣ ግራ ተጋባ፡፡ በአዳራሹ ውስጥ ያለው ብርሃን ደብዛዛ ቢሆንም እጆቹ የተነከሩበትን ደም ሳትመለከት ልጅቱ የሚሰማት ስሜት አልጋ እንደሚያስከለክለው እርግጠኛ ነበር፡፡
“መጀመሪያ ክፍሉን ልየዋ፡፡” አላት በተቻለው ራሱን ለመግዛት
እየጣረ::
'ተከተለኝ ለማለት ጭንቅላቷን መታ አደረገችና ፊቷን መልሳ ወደ ጓዳ ገባች፡፡ ተከተላት:: ከሚከራየት ክፍል ሲደርሱ በሩን ከፍታ፣ መብራቱን አብርታ ፈቀቅ አለችለት፡፡ ወደ ክፍሉ ገባና ቀልጠፍ ብሎ መብራቱን አጠፋው:: ወዲያው የገንዘብ ቦርሳውን አውጥቶ ከመተላለፊያው በሚመጣው ስስ ብርሃን የአስር ብር ኖት አውጥቶ ሰጣት፡፡
“መልሱን ያዥው እ… መታጠቢያ ቤት ይኖራል?”
ያው!” አለች ከአስር ብሩ የሚመላሶው አራት ብር የእርሷ መሆኑን ስታውቅ ፈገግ ብላ፡፡
መታጠቢያ ቤት ገብቶ በደም የተበከላ ልብሱንና ሰውነቱን አጣጥቦ ወደተከራየ ክፍል ተመለሰ፡፡ አልጋው ላይ በጀርባው ተንጋሎ አይኖቹን ከደነ፡፡ እንቅልፍ ግን አልጎበኘውም፡፡ ሰውነቱ ሊረጋጋለት አልቻለም፡፡
ምንድነው ነገሩ የተዘበራረቀበትን ሁኔታ ትርጉም ሊሰጠው ተጣጣረ:: ሴትዮዋ ከየት መጣች? ሰካራሟ ማነች? ያለጥርጥር የካልቨርትን አድራሻ ትፈልጋለች፡፡ ለዚህም ነው የምሥራችን የገደለቻት:: ግን እሱን ለምን ተወችው? ሠውነቱው በቻ ሳይሆን ሕይወቱን ለማትረፍ የሌላ ስው ሕይወት ለምን አጠፋች? እሷ ማነች? በአውሬው ውስጥ ለውስጥ አለመግባባትና መከፋፈል አለ ማለት ነው? አንደኛው ወገን ሊያጠፋው
ሲፈልግ የተቀረው ወገን ሞቱን አይሻም ማለት ነው? ግን ለምን? የእርሱ
መኖር ማንን ይጠቅማል? እንዴት? የምሥራች መሞትስ ምን ይጨምራል?
ሴትየዋ ማነች? ሰውየውስ? ሰውየው በምሥራች ሞት ለምን ተደናገጠ?
እርሱንስ ለምን ሊገለው ሞከረ? ሴትየዋ ከጀርባው ባትቀድመው ጨርሶት
ነበር'ኮ!”
የምሥራችን ሳይሆን የእርሱን መጥፋትና መሞት የሚሻ ወገን አሉ ማለት ነወ፡፡ ያለ ጥርጥር ይህኛው ወገን ነው ከብርሃምን የገደለው:: ግን እነማን ናቸው? ምንድነው የሚፈልጉት? ግልፅ ነው:: ሁሉም የሚፈልጉት ካልቨርትን ነው፡፡ የካልቨርትን አድራሻ የምታውቅ የምሥራች ብቻ ነበረች፡፡ ሊያስፈራራት ቢላውን ሲያወጣባት ምንድን ነበር ያላችው የምሥራች?'
“አትነካኝም! ጫፌን ብትነካኝ ዮሴፍ ምን እንደሚያደርግ ታውቃላችሁ! ያወጣዋል ምሥጢራችሁን ያውጣዋል! "
አዎ…እንደጠረጠረው ካልቨርት ይዞት የተሸሸገው ምሥጢር ኣለ፡፡አውሬው የምሥጢሩን መጠበቅ ለማረጋገጥ ሲል ካልቨርትን እጁ ማስገባት ቢፈልግም የምሥራችን ለመተናኮል ያልደፈረው ካልቨርት ምሥጢሩን በይፋ ለማውጣት እንዳይሰቀለው በመፍራት መሆን አለበት፡፡ አወሬው የካልቨርት አባራሪ ይምሰል እንጅ እስረኛውም ነው፡፡ ምክንያቱም ካልቨርት የአውሬውን ምሥጢር በመዳፉ አድርጓል፡፡ የአብርሃም አደራ ታወሰው
«ካልቨርትን አግኝ... ካልቨርትን» አብርሃም ትክክል ነው፡፡ ቁልፉ ያለው
ከዚያ ነው፡፡ ካልቨርት የያዘውን ምሥጢር በጁ ያገባ ሁሉ የአውሬኑን እፍንጫ መሰነግ ይችላል፡፡ ግን ምንድነው ምሥጢሩ? የት ነው ካልቨርት...?
የምሥራች ነበረች ኣድራሻውን የምታውቅ፡፡ ሞታለች፡፡ ሌላ ማን አለ? እርሱ ራሱ ! ነግራዋለች፡፡ አዎ… የካልቨርትን ኣድራሻ ነግራዋለች፡፡ እሱ ብቻ ነው የካልቨርትን አድራሻ የሚያውቅ
“እ…እማዬጋ..ድራዳዋ::"
እማዬጋ... ድሬዳዋ.. የት ናቸው እማዬ? እናቷ? ድሬዳዋ ድሬዳዋ የት?
ናትናኤል በተከራየው የሆቴል ክፍል ወስጥ በጀርባወ አልጋው ላይ እንደተንጋለሉ ዓይኖቹን ኮርኒሱ ላይ ተክሎ ቀረ፡፡
በድሬዳዋ እየተዘዋወረ “የምሥራች እናት እያለ አይፈልግ! ስማቸውን እንኳን አያውቅም፡፡ የምሥራች ይልማ:: እርግጥ የምሥራችን አባት ስም ያውቃል አቶ ይልማ... አስር አለቃ ይልማ ቄስ ይልማ
ፈጣሪ ይወቅ! አባቷን ካገኘ ግን እናቷን አገኘ ማለት ነው:: አብረው አይኖሩ
እንደሆንስ? ቢሆንም የእናቷን አድራሻ ሳያውቁ አይቀሩም ግን አባቷንስ ቢሆን “አቶ ይልማ” እያለ በድሬዳዋ ከተማ ቢዞር አባቷን እንዴት ማግኘት ይችላል? የአባታቸውን ስም ቢያውቅ ጥሩ ነበር፡፡ ያንን እንኳን ማግኘት ይችላል፡፡ እ… ተመልሶ ወደ ሆቴሏ ሄዶ የንግድ ፈቃዷ ላይ ማንበብ ይችላል፡፡ የአባቷና የአያቷ ስም ይኖራል፡፡ ግን ከአሁን ወዲያ ወደዚያ
አቅሪቢያ መሄድ በገዛ እጁ መንጠልጠል ነው:: ሰው ቢልክስ? ማንን?
አንዱን የሠፈር ስራፈት ጎረምሳ አምስት ብር ቢያሳየው ሄዶ ያነብለታል
በዚህ ከደገኛ ሰዓት የላከው ወጣት የንግድ ፈቃዷን ተጠግቶ ፊደል ሲቆጥር
“ምንድነው የምትሰራው?” ብለው
👍1
ቢይዘትስ? . “ምራ” ቢሉትስ?
አስከትሏቸው ከተፍ ቢልስ? አ! አ! አ አይሆንም፡፡ ሌላ ምርጫ መኖር
አለበት፡፡ የንግድ ፈቃድ ግብር... አገር ውስጥ ገቢ... አዎ እዚያም የአያቷ
ስም ይኖራል፡፡ ግን አገር ውስጥ ገቢ የሚያውቀውና ፋይሏን አውጥቶ
የሚያይለት ወይ የሚያሳየው የለውም፡፡ ሂዶ ፋይሏን ቢጠይቅ ደግሞ
ጥርጣሬ መፍጠር ነው:: “ለምን ፈለግኸው? ምንድነህ አንተ?” ቢሉት ምን ሊመልስ? አ! አ! አይሆንም፡፡ ሌላ ምርጫ ሌላ መፍጠን ኣለበት!
መቅደም አለበት! ቶሎ ወዴ ድሬዳዋ ቶሎ ወደ ካልቨርት... ቶሎ ወደ ምሥጢሩ… ቶሎ ቶሎ ! የአባቷ ሙሉ ስም ማነው? ይልማ... ይልማ ማን?........
💫ይቀጥላል💫
አስከትሏቸው ከተፍ ቢልስ? አ! አ! አ አይሆንም፡፡ ሌላ ምርጫ መኖር
አለበት፡፡ የንግድ ፈቃድ ግብር... አገር ውስጥ ገቢ... አዎ እዚያም የአያቷ
ስም ይኖራል፡፡ ግን አገር ውስጥ ገቢ የሚያውቀውና ፋይሏን አውጥቶ
የሚያይለት ወይ የሚያሳየው የለውም፡፡ ሂዶ ፋይሏን ቢጠይቅ ደግሞ
ጥርጣሬ መፍጠር ነው:: “ለምን ፈለግኸው? ምንድነህ አንተ?” ቢሉት ምን ሊመልስ? አ! አ! አይሆንም፡፡ ሌላ ምርጫ ሌላ መፍጠን ኣለበት!
መቅደም አለበት! ቶሎ ወዴ ድሬዳዋ ቶሎ ወደ ካልቨርት... ቶሎ ወደ ምሥጢሩ… ቶሎ ቶሎ ! የአባቷ ሙሉ ስም ማነው? ይልማ... ይልማ ማን?........
💫ይቀጥላል💫
👍2
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ዴሪክ ዊሊያምስ ከሀይ ሆፕ ካፌው ወጥቶ ስምንት ብሎክ ወደሚቀርበው ሴንተሊና ውስጥ ወደሚገኘው ቢሮው ለመሄድ መኪናውን ሲያሽከረክር ከጠዋቱ አራት ሰዓት አልፎ ነበር። ቢሮው 12 ጫማ በ 8 ጫማ ስፋት ያለው ሆኖ መስኮት አልባ ነው፡፡ ነገር ግን ኪራዩ በጣም ርካሽ ስለሆነ እና የዋይፋይ ኢንተርኔቱ ጥሩ ስለሆነ ቢሮው ተስማምቶታል፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ከፎቁ ሥር የሚገኙት ወዳጆቹ የብረት ጎማ ስላላቸው ደምበኞቹ አስቸጋሪ በሚሆኑበት ጊዜ አስፈላጊውን እገዛ ያደርጉለታል፡፡
የአሁኗ ደንበኛው ያን ያክል አስቸጋሪ አይደለችም፡፡ ለሦስት ሰዓታት ያህል ቁጭ ብላ ስታወራው ዴሪክ ሦስት ነገሮች ለመገንዘብ ችሏል፡፡
የመጀመሪያው ነጥብ በትክክል እጁ ላይ ያለውን ካርዶችን በአግባቡ የሚጫወትበት ከሆነ በሥራው በጣም ብዙ ገንዘብ ያገኝበታል፡፡
ሁለተኛው ነገር ደግሞ ዕድሉ ከሆነ እና ከተሳካለት የድሮ ጠላቶቹ የሆኑትን የሎስ አንጀለስ ፖሊስ ዲፓርትመንት መበቀል ያስችለዋል::
ሦስተኛው ነገር ደግሞ ይሄ ጉዳይ ራሱን አደጋ ውስጥ ሊከተው የሚችል ነገር መሆኑ ነው።
ከሦስቱ ጉዳዩች በዋነኝነት የሳበው ነገር ቢኖር የሦስተኛው ጉዳይ ነው:: በጣም ከረዥም ጊዜ በኋላ ራሱ ላይ አደጋን የሚፈጥር ጉዳይ ሊገጥመው ነው። ትዳር ከመመስረቱ በፊት እንደዚህ ያሉ አደገኛ ጉዳዮች ላይ ነበር ይሰራ የነበረው። እናም ዛሬ ዶክተር ኒኪ ሮበርትስ
ጉዳይዋን እንዲመረምርላት ስታናግረው የድሮው ማንነቱን ምን ያህል እንደናፈቀው
ነበር የተረዳው።
ማታ ላይ የጠጣው መጠጥ እና ጠዋት ላይ የበላው ቁርስ ሆዱ ውስጥ ቁጭ ስላለበት፣ እንዲፈጭለት ሁለት የአልካ ሲልትዘርን በትልቅ ብርጭቆ ውስጥ በሚገኝ የቧምቧ ውሃ ላይ ጨምሮ ጭልጥ አድርጎ ጠጣው። ከዴስኩ
ውስጥም የድሮ የማስታዋሻ ደብተር አውጥቶ መፃፍ ጀመረ፡፡ እንደ
ሁልጊዜም ሁሉ ሠረዝ ሠረዝ እያደረገ ከማንኛውም ደምበኛው የመጀመሪያ
ስብሰባ ካደረገ በኋላ በዚህ መልኩ ይፅፋል።
ወዲያውንም ገፆችን እየሞላ ማስታወሻውን መያዝ ጀመረ።
ኒኪ ሮበርትስ የምታስገርም ሴት ናት። በተለይ ደግሞ ለፖሊሶች ያልነገራቻቸውን ሚስጥሮቿን ለእሱ መንገሯ ጉዳይዋን ከፖሊሶቹ ቀድሞ ሊቋጭላት ያስችለዋል። እሷ እንዲፈታላት የፈለገችውን ነገር ለሁለት ከፍሎ ምርመራ መጀመሩ
ገቢውን ስለሚጨምርለት የተደራደራት። እሷም በእሱ ሀሳብ ሙሉ በሙሉ ተስማምታ ሌሎች ሰዎችን
በዚህ መልኩ ነበር ከሚያስከፍለው በእጥፍ ሂሳብ ሲጠይቃት ጭምር ያለማንገራገር ለዚያውም ከነ ቦነሱ ነበር ቼክ የፃፈችለት።
“ባልሽ ከትዳር ውጪ ስላለው የፍቅር ግንኙነት ለማወቅ ትፈልጊያለሽ አይደል? ማለትም ሴትየዋ ማን እንደሆነች፣ እንዴት እንደተገናኙ እና ከእሷ ጋር የተያያዙትን ነገሮች ሁሉ ማወቅ እፈልጋለሁ ብለሻል?” ብሎ ጠየቃት።
“ልክ ነው” ብላ መለሰችለት ኒኪ
“መልካም እሱ የመጀመሪያው ጉዳይሽ ነው። ሌላኛው ደግሞ ግድያዎቹን
በተመለከተ እና አንቺ ላይ የግድያ ማስፈራሪያ እየተደረገብሽ ስላለ ጉዳይ
ነው። ከእነዚህ ግድያዎች በስተጀርባ ያለውን ሰው ልታውቂ ትፈልጊያለሽ።
ይሄ ደግሞ እኔ የኤል.ኤ.ፒ.ዲ ሥራን እንድሠራላቸው ትፈልጊያለሽ ማለት
ነው?”
“በትክክል”
“ይሄ ደግሞ ሁለተኛው ጉዳይሽ ነው” ብሎ ለእያንዳንዱ ጉዳዮቿ ዋጋ አውጥቶ ሲጠይቃት ኒኪ የወር ወጪውን በእጥፍ ዋጋ ነበር ቼኳ ላይ ፅፋ የሰጠችው። በዚህም የተነሳ ይህቺን ሴት በእውነቱ ሳይወዳት አይቀርም፡፡
ቢሮው ገብቶ ስለ ሁለቱ ጉዳዮች ሲያስብ የመጀመሪያው ባሏ ውሽማ ጉዳይ ገንዘብን የሚያልብበት ጉዳዩ እንደ ሆነ ገባው:: ምክንያቱም የኤል.ኤፒዲ ፖሊሶች ስለ ዶውግ ውሽማ ማንነት የሚያጣሩበት አንድም ምክንያት የላቸውም እና እሱ ጉዳዩን እስከፈለገው ጊዜ ድረስ በመጎተት የማያቋርጥ የገቢ ምንጩ ማድረግ ይችላል። በምዕራባዊ ሎስ አንጀለስ ውስጥ በዝሙት ዙሪያ ያሉ ጉዳዮች በሙሉ በጣም ምርጥ የገቢ ምንጭ የሚያስገኙለት ጉዳዮቹ ናቸው እና አምላኩን ያመሰግናል።
በግድያዎቹ ዙሪያ ላይ የሚያደርገው የግል ምርመራ ግን ያን ያህል የብዙ ጊዜው አስተማማኝ የገቢ ምንጩ ላይሆን ይችላል። ምክንያቱም
ምናልባት ይህንን ወር እንኳን ሳይጨርስ ኤል.ኤ.ፒ.ዲ የሊዛ ፍላንገን እና
የትሬቨን ሬይሞንድን ገዳዮችን ይዘው ለፍርድ ማቅረብ ይችላሉ። ምናልባት
ፖሊሶቹ በፍጥነት ጉዳዩን እንዳይቋጩ የሚያደርጋቸው ነገሮች ቢኖሩ
ዶክተሯን በመኪና ገጭቶ ሊያመልጥ የሞከረውን ገዳይ መከታተል ችላ
ማለታቸው አንደኛው ነው፡፡ ሁለተኛው ነገር ደግሞ ኒኪ በፖሊሶቹ ላይ
ሙሉ እምነት ስለሌላቸው የግድያ ማስፈራሪያ የኢ-ሜይል መልዕክቷን
እንኳን አምጥታ ለእሱ (ላዊሊያምስ) ማስረከቧ ነው።
ይሄ ደግሞ ሌላ ምርጥ ምልክት ነው፡፡ በጣም ብዙ መረጃዎችን በጉዳዩ
ዙሪያ መሰብሰብ እስከቻለ ድረስ ከኤል.ኤ.ፒ.ዲ ቀድሞ ምርመራውን በድል ማጠናቀቅ የሚችልበትን ዕድል ይፈጥርለታል፡፡
ከባሏ ውሽማ ይልቅ የሊዛ እና የትሬይ ግድያዎች ጉዳይ እሱን በደንብ የሳበው ሌላኛው ነገር ነው:: እንደ ሁሉም የሎስ አንጀለስ ነዋሪ ሁሉ ዴሪክም ቢሆን የግድያዎቹን ዜናዎች በደንብ ይከታተል ነበር፡፡ የኒኪ ሮበርትስ ታካሚ የሆነችው ቆንጆዋ ሞዴል ሊዛ ፍላንገን በአሰቃቂ ሁኔታ ሰውነቷ ተቆራርጦ እና ልቧ ላይ በጩቤ ተወግታ ህይወቷ አልፏል። ሊዛ
ትሬይ ሊዛ አፍሪካ አሜሪካዊው
ከተገደለች ከሦስት ቀናት በኋላም
በተገደለችበት በተመሳሳይ ሁኔታ ለመገደል በቅቷል። በመጀመሪያ ላይ በሊዛ ጥፍር ውስጥ የተገኘው የሞተ ሰው ህዋስን በማስመልከት ዞምቢው ነፍሰ ገዳይ በሚል ርዕስ በየማህበራዊ ገፆች ላይ ሲሰራጭ የነበረው ዜና
በመጨረሻ ላይም በዋነኛ የሚዲያ ተቋማት ላይ በዜና መልክ ቀርቦም
ተመልክቶታል፡፡ ሰዎች በእውነተኛው ዓለም ላይ እንደዚህ አይነት ነገር አለ
ብለው ማመናቸውን በወቅቱ ዴሪክን አስቆት ነበር፡፡ ያም ቢሆን ግን እስከ
አሁን ድረስ ጉዳዩን አወሳስቦታል።
“እና እስከ አሁን ድረስ ኤል.ኤ.ፒ.ዲ በግድያው ጠርጥሮ የያዘው አንድም
ሰው የለማ?” ብሎ ዴሪክ ኒኪን ጠየቋት ነበር፡፡
“እስከ አሁን ድረስ የለም። እንዲያውም አንደኛው ጆንሰን የተባለው መርማሪ ፖሊስ እኔን እንደ ገዳይ ሁሉ ይጠረጥረኛል፡፡ ባገኘኝ እና ባወራኝ
ቁጥርም እኔን የሚያወራኝ ልክ እንደ ወንጀለኛ ነው::”
“ይሄንን ባያደርግ አይገርመኝም፡፡ ሁሉም ፖሊሶች ባለጌዎች ናቸው፡፡” ብሎ ዴሪክ መለሰላት፡፡
“ሁሉም እንኳን አይደሉም ብላ ኒኪ አሰበች፡፡ ይህን ሀሳቧን ግን ለዊሊያምስ አልነገረችውም። በመቀጠልም ዊሊያምስን ያስገረመ አንድ ነገር
እንደደበቀቻቸው ነገረችው።
“ብራንዶን ግሮልሽ የሚባል ልጅ አውቅ እንደሆነ ጠይቀውኝ ነበር። ነገር
ግን አላውቅም ብዬ ነው የመለስኩላቸው፡፡ ልጁን አውቀው ነበር። ባለቤቱ እኔ ህክምና እንዳደርግለት ወደ እኔ ቢሮ ይዞት መጥቶ ነበር::”
“ለምንድነው ስለ እዚህ ልጅ የጠየቁሽ? አንቺስ ለምን ዋሸሻቸው?” ብሎ
ዊሊያምስ ጠየቃት፡፡
ኒኪም ትከሻዋን ሰበቀች እና “ለምን እንደጠየቁኝ አላውቅም። ምናልባት
ግን ልጁ ከግድያዎች ጋር የተያያዘ ነገር አለው ብለው እንደሚያስቡ ገምቻለሁ። ይሄውልህ ይሄ ብራንዶን የተባለ ልጅ እንደዚህ አይነት ነገርን የማድረግ አቅም የለውም፡፡ ልጁ በጣም ጨዋ እና መልካም ልጅ ነበር::" ብላ ፈገግ በማለት
አሁን ላይ ሳስበው ግን ልጁን አላውቀውም ብዬ የዋሸሁለት ከእነርሱ
ልከላከለው አስቤ ይመስለኛል”
“ፖሊሶቹ መዋሸትሽን ቢደርሱበት መረጃን በመደበቅ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ዴሪክ ዊሊያምስ ከሀይ ሆፕ ካፌው ወጥቶ ስምንት ብሎክ ወደሚቀርበው ሴንተሊና ውስጥ ወደሚገኘው ቢሮው ለመሄድ መኪናውን ሲያሽከረክር ከጠዋቱ አራት ሰዓት አልፎ ነበር። ቢሮው 12 ጫማ በ 8 ጫማ ስፋት ያለው ሆኖ መስኮት አልባ ነው፡፡ ነገር ግን ኪራዩ በጣም ርካሽ ስለሆነ እና የዋይፋይ ኢንተርኔቱ ጥሩ ስለሆነ ቢሮው ተስማምቶታል፡፡ በዚያ ላይ ደግሞ ከፎቁ ሥር የሚገኙት ወዳጆቹ የብረት ጎማ ስላላቸው ደምበኞቹ አስቸጋሪ በሚሆኑበት ጊዜ አስፈላጊውን እገዛ ያደርጉለታል፡፡
የአሁኗ ደንበኛው ያን ያክል አስቸጋሪ አይደለችም፡፡ ለሦስት ሰዓታት ያህል ቁጭ ብላ ስታወራው ዴሪክ ሦስት ነገሮች ለመገንዘብ ችሏል፡፡
የመጀመሪያው ነጥብ በትክክል እጁ ላይ ያለውን ካርዶችን በአግባቡ የሚጫወትበት ከሆነ በሥራው በጣም ብዙ ገንዘብ ያገኝበታል፡፡
ሁለተኛው ነገር ደግሞ ዕድሉ ከሆነ እና ከተሳካለት የድሮ ጠላቶቹ የሆኑትን የሎስ አንጀለስ ፖሊስ ዲፓርትመንት መበቀል ያስችለዋል::
ሦስተኛው ነገር ደግሞ ይሄ ጉዳይ ራሱን አደጋ ውስጥ ሊከተው የሚችል ነገር መሆኑ ነው።
ከሦስቱ ጉዳዩች በዋነኝነት የሳበው ነገር ቢኖር የሦስተኛው ጉዳይ ነው:: በጣም ከረዥም ጊዜ በኋላ ራሱ ላይ አደጋን የሚፈጥር ጉዳይ ሊገጥመው ነው። ትዳር ከመመስረቱ በፊት እንደዚህ ያሉ አደገኛ ጉዳዮች ላይ ነበር ይሰራ የነበረው። እናም ዛሬ ዶክተር ኒኪ ሮበርትስ
ጉዳይዋን እንዲመረምርላት ስታናግረው የድሮው ማንነቱን ምን ያህል እንደናፈቀው
ነበር የተረዳው።
ማታ ላይ የጠጣው መጠጥ እና ጠዋት ላይ የበላው ቁርስ ሆዱ ውስጥ ቁጭ ስላለበት፣ እንዲፈጭለት ሁለት የአልካ ሲልትዘርን በትልቅ ብርጭቆ ውስጥ በሚገኝ የቧምቧ ውሃ ላይ ጨምሮ ጭልጥ አድርጎ ጠጣው። ከዴስኩ
ውስጥም የድሮ የማስታዋሻ ደብተር አውጥቶ መፃፍ ጀመረ፡፡ እንደ
ሁልጊዜም ሁሉ ሠረዝ ሠረዝ እያደረገ ከማንኛውም ደምበኛው የመጀመሪያ
ስብሰባ ካደረገ በኋላ በዚህ መልኩ ይፅፋል።
ወዲያውንም ገፆችን እየሞላ ማስታወሻውን መያዝ ጀመረ።
ኒኪ ሮበርትስ የምታስገርም ሴት ናት። በተለይ ደግሞ ለፖሊሶች ያልነገራቻቸውን ሚስጥሮቿን ለእሱ መንገሯ ጉዳይዋን ከፖሊሶቹ ቀድሞ ሊቋጭላት ያስችለዋል። እሷ እንዲፈታላት የፈለገችውን ነገር ለሁለት ከፍሎ ምርመራ መጀመሩ
ገቢውን ስለሚጨምርለት የተደራደራት። እሷም በእሱ ሀሳብ ሙሉ በሙሉ ተስማምታ ሌሎች ሰዎችን
በዚህ መልኩ ነበር ከሚያስከፍለው በእጥፍ ሂሳብ ሲጠይቃት ጭምር ያለማንገራገር ለዚያውም ከነ ቦነሱ ነበር ቼክ የፃፈችለት።
“ባልሽ ከትዳር ውጪ ስላለው የፍቅር ግንኙነት ለማወቅ ትፈልጊያለሽ አይደል? ማለትም ሴትየዋ ማን እንደሆነች፣ እንዴት እንደተገናኙ እና ከእሷ ጋር የተያያዙትን ነገሮች ሁሉ ማወቅ እፈልጋለሁ ብለሻል?” ብሎ ጠየቃት።
“ልክ ነው” ብላ መለሰችለት ኒኪ
“መልካም እሱ የመጀመሪያው ጉዳይሽ ነው። ሌላኛው ደግሞ ግድያዎቹን
በተመለከተ እና አንቺ ላይ የግድያ ማስፈራሪያ እየተደረገብሽ ስላለ ጉዳይ
ነው። ከእነዚህ ግድያዎች በስተጀርባ ያለውን ሰው ልታውቂ ትፈልጊያለሽ።
ይሄ ደግሞ እኔ የኤል.ኤ.ፒ.ዲ ሥራን እንድሠራላቸው ትፈልጊያለሽ ማለት
ነው?”
“በትክክል”
“ይሄ ደግሞ ሁለተኛው ጉዳይሽ ነው” ብሎ ለእያንዳንዱ ጉዳዮቿ ዋጋ አውጥቶ ሲጠይቃት ኒኪ የወር ወጪውን በእጥፍ ዋጋ ነበር ቼኳ ላይ ፅፋ የሰጠችው። በዚህም የተነሳ ይህቺን ሴት በእውነቱ ሳይወዳት አይቀርም፡፡
ቢሮው ገብቶ ስለ ሁለቱ ጉዳዮች ሲያስብ የመጀመሪያው ባሏ ውሽማ ጉዳይ ገንዘብን የሚያልብበት ጉዳዩ እንደ ሆነ ገባው:: ምክንያቱም የኤል.ኤፒዲ ፖሊሶች ስለ ዶውግ ውሽማ ማንነት የሚያጣሩበት አንድም ምክንያት የላቸውም እና እሱ ጉዳዩን እስከፈለገው ጊዜ ድረስ በመጎተት የማያቋርጥ የገቢ ምንጩ ማድረግ ይችላል። በምዕራባዊ ሎስ አንጀለስ ውስጥ በዝሙት ዙሪያ ያሉ ጉዳዮች በሙሉ በጣም ምርጥ የገቢ ምንጭ የሚያስገኙለት ጉዳዮቹ ናቸው እና አምላኩን ያመሰግናል።
በግድያዎቹ ዙሪያ ላይ የሚያደርገው የግል ምርመራ ግን ያን ያህል የብዙ ጊዜው አስተማማኝ የገቢ ምንጩ ላይሆን ይችላል። ምክንያቱም
ምናልባት ይህንን ወር እንኳን ሳይጨርስ ኤል.ኤ.ፒ.ዲ የሊዛ ፍላንገን እና
የትሬቨን ሬይሞንድን ገዳዮችን ይዘው ለፍርድ ማቅረብ ይችላሉ። ምናልባት
ፖሊሶቹ በፍጥነት ጉዳዩን እንዳይቋጩ የሚያደርጋቸው ነገሮች ቢኖሩ
ዶክተሯን በመኪና ገጭቶ ሊያመልጥ የሞከረውን ገዳይ መከታተል ችላ
ማለታቸው አንደኛው ነው፡፡ ሁለተኛው ነገር ደግሞ ኒኪ በፖሊሶቹ ላይ
ሙሉ እምነት ስለሌላቸው የግድያ ማስፈራሪያ የኢ-ሜይል መልዕክቷን
እንኳን አምጥታ ለእሱ (ላዊሊያምስ) ማስረከቧ ነው።
ይሄ ደግሞ ሌላ ምርጥ ምልክት ነው፡፡ በጣም ብዙ መረጃዎችን በጉዳዩ
ዙሪያ መሰብሰብ እስከቻለ ድረስ ከኤል.ኤ.ፒ.ዲ ቀድሞ ምርመራውን በድል ማጠናቀቅ የሚችልበትን ዕድል ይፈጥርለታል፡፡
ከባሏ ውሽማ ይልቅ የሊዛ እና የትሬይ ግድያዎች ጉዳይ እሱን በደንብ የሳበው ሌላኛው ነገር ነው:: እንደ ሁሉም የሎስ አንጀለስ ነዋሪ ሁሉ ዴሪክም ቢሆን የግድያዎቹን ዜናዎች በደንብ ይከታተል ነበር፡፡ የኒኪ ሮበርትስ ታካሚ የሆነችው ቆንጆዋ ሞዴል ሊዛ ፍላንገን በአሰቃቂ ሁኔታ ሰውነቷ ተቆራርጦ እና ልቧ ላይ በጩቤ ተወግታ ህይወቷ አልፏል። ሊዛ
ትሬይ ሊዛ አፍሪካ አሜሪካዊው
ከተገደለች ከሦስት ቀናት በኋላም
በተገደለችበት በተመሳሳይ ሁኔታ ለመገደል በቅቷል። በመጀመሪያ ላይ በሊዛ ጥፍር ውስጥ የተገኘው የሞተ ሰው ህዋስን በማስመልከት ዞምቢው ነፍሰ ገዳይ በሚል ርዕስ በየማህበራዊ ገፆች ላይ ሲሰራጭ የነበረው ዜና
በመጨረሻ ላይም በዋነኛ የሚዲያ ተቋማት ላይ በዜና መልክ ቀርቦም
ተመልክቶታል፡፡ ሰዎች በእውነተኛው ዓለም ላይ እንደዚህ አይነት ነገር አለ
ብለው ማመናቸውን በወቅቱ ዴሪክን አስቆት ነበር፡፡ ያም ቢሆን ግን እስከ
አሁን ድረስ ጉዳዩን አወሳስቦታል።
“እና እስከ አሁን ድረስ ኤል.ኤ.ፒ.ዲ በግድያው ጠርጥሮ የያዘው አንድም
ሰው የለማ?” ብሎ ዴሪክ ኒኪን ጠየቋት ነበር፡፡
“እስከ አሁን ድረስ የለም። እንዲያውም አንደኛው ጆንሰን የተባለው መርማሪ ፖሊስ እኔን እንደ ገዳይ ሁሉ ይጠረጥረኛል፡፡ ባገኘኝ እና ባወራኝ
ቁጥርም እኔን የሚያወራኝ ልክ እንደ ወንጀለኛ ነው::”
“ይሄንን ባያደርግ አይገርመኝም፡፡ ሁሉም ፖሊሶች ባለጌዎች ናቸው፡፡” ብሎ ዴሪክ መለሰላት፡፡
“ሁሉም እንኳን አይደሉም ብላ ኒኪ አሰበች፡፡ ይህን ሀሳቧን ግን ለዊሊያምስ አልነገረችውም። በመቀጠልም ዊሊያምስን ያስገረመ አንድ ነገር
እንደደበቀቻቸው ነገረችው።
“ብራንዶን ግሮልሽ የሚባል ልጅ አውቅ እንደሆነ ጠይቀውኝ ነበር። ነገር
ግን አላውቅም ብዬ ነው የመለስኩላቸው፡፡ ልጁን አውቀው ነበር። ባለቤቱ እኔ ህክምና እንዳደርግለት ወደ እኔ ቢሮ ይዞት መጥቶ ነበር::”
“ለምንድነው ስለ እዚህ ልጅ የጠየቁሽ? አንቺስ ለምን ዋሸሻቸው?” ብሎ
ዊሊያምስ ጠየቃት፡፡
ኒኪም ትከሻዋን ሰበቀች እና “ለምን እንደጠየቁኝ አላውቅም። ምናልባት
ግን ልጁ ከግድያዎች ጋር የተያያዘ ነገር አለው ብለው እንደሚያስቡ ገምቻለሁ። ይሄውልህ ይሄ ብራንዶን የተባለ ልጅ እንደዚህ አይነት ነገርን የማድረግ አቅም የለውም፡፡ ልጁ በጣም ጨዋ እና መልካም ልጅ ነበር::" ብላ ፈገግ በማለት
አሁን ላይ ሳስበው ግን ልጁን አላውቀውም ብዬ የዋሸሁለት ከእነርሱ
ልከላከለው አስቤ ይመስለኛል”
“ፖሊሶቹ መዋሸትሽን ቢደርሱበት መረጃን በመደበቅ
👍7
በሚል ወንጀል ሊከሱሽ እንደሚችሉ ታውቂያለሽ?” ብሎ ተኮሳትሮ ጠየቃት፡፡
“አውቃለው ግን ደንታ የለኝም” ብላ ኒኪ ኮስተር ብላ መልሳለት በመቀጠልም
“ምን መሰለህ እውነታው ሚ/ር ዊሊያምስ? ፖሊሶቹን አላምናቸውም”
አለችው። ይህንን ከእሷ የሰማው ዴሪክ ዊሊያምስም ተነስቶ ቢጨብጣት እና
እኔም አላምናቸውም ቢላት ደስ ባለው ነበር፡፡
“እኔን ግን ታምኚኛለሽ አይደል?” ፈገግ ብሎ ጠየቃት፡፡
“ባላምንብህ ለምን ብዬ ነው የጠየቅከውን ሳልከራከርህ የምከፍልህ” ብላ ኒኪ በፈገግታ መለሰችለት፡፡
“ልክ ነሽ” ብሎ ዊሊያምስ ፈገግ አለ እና “እሺ ይሄንን ብራንዶን የተባለ ልጅን ለመጨረሻ ጊዜ ያገኘሺው መቼ ነው?” ብሎ ጠየቃት፡፡
“ሁ ረዥም ጊዜ አልፎታል ካገኘሁት፡፡ ዓመት አይሆነውም ብለህ ነው? አዎን ከቦስተን ደውሎልኝ ነበር፡፡ አደንዛዥ ዕፅን በድጋሚ መጠቀም ጀምሮ ነበር። በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ነበር ወደ እኔ የደወለው” ብላ ኒኪ መለሰችለት፡፡
“ብራንዶን ሞቷል ብለሽ ታስቢያለሽ?” ብሎ ዊሊያምስ ጠየቃት፡፡
ኒኪም ትከሻዋን ከሰበቀች በኋላ “ሊሞት ይችላል። ግን ስለ እሱ እርግጠኛ ሆኜ ልነግርህ አልችልም”
“እሺ አሁን ደግሞ በግድያው ዙሪያ ላይ ምርመራውን ስለሚያደርጉት
ፖሊሶች ንገሪኝ እስቲ?” አላት፡፡
ኒኪ በረዥሙ አየር ስባ ከተቀመጠች በኋላ መርማሪ ፖሊስ ሚክ ጆንስን ለእሷ ጥሩ አመለካከት እንደሌለው እና እሷንም እንደወንጀለኛ እየቆጠራት እንደሆነ ከነገረችው በኋላ “ባይገርምህ እኔን ገጭቶ ለማምለጥ ሙከራ ስላደረገው ላንድክሩዘር መኪና እና ስላዳነኝ ቀዩ የስፖርት መኪና ሹፌር ሁሉ ፈጥሬ እያወራሁት እንዳለ አምኖ ነው በቁጣ እየወነጀለ ያወራኝ፡፡ ባልደረባው መርማሪ ፖሊስ ሉው ጉድማን ግን ምክንያታዊ ሰው ይመስለኛል” ብላ የጉድማንን ስም ስትጠራ የኒኪ ፊት በፈገግታ ሲፈካ ዴሪክ
ዊሊያምስ ተመለከተ፡፡ “ብቻ እሱ ይለያል” አለችው፡፡
“እሱ በምን መልኩ ነው ይለያል ብለሽ ለመናገር የቻልሽው?”
“እያንዳንዱ ነገሩ። ትሁት ነው፤ ጠንካራ ሠራተኛ ነው፤ የተማረ እና ግልፅ ነገር ነው” ብላ ኒኪ መለሰችላት። እንደዚህ ሆኖም ግን እኮ የምርመራ ጉዳያቸውን ከጫፍ አላደረሰም” ብሎ ዊሊያምስ አሳሰባት፡፡
“ይሆናል” ብላ ኒኪ ቅር እያላት ዊሊያምስ ባነሳው ሀሳብ ተስማማች እና “እርግጥ ነው መዘግየት ይታይበታል፡፡ እሱ እንደነገረኝ ከሆነ ሊዛ ፍላንገን ሊገድል የመጣው ነፍሰ ገዳይ በስህተት እኔን መስላው ነው ሊገድላት የቻለው። ምክንያቱም በወቅቱ እሷ የእኔን የዝናብ ኮት አድርጋ ነበር። ምንም እንኳን እንደ እሷ በጣም ቆንጆ ባልሆንም ቁመታችን
ተመሳሳይ ስለነበረ ነፍሰ ገዳዩ እኔኸ መስዬው እሷን እንደገደላት ግምቱን
አስቀምጦልኛል።”
“ሊያስኬድ ይችላል” ብሎም ዴሪክፀ ዊሊያምስ መለሰላት።
በመቀጠልም ኒኪ ከመኝታ ክፍሏ ውስጥ ስለተሰረቀው ፎቶግራፍ ነገረችው። አስከትላም ጥቁር ላንድሮቨር ገጭቶ ሊገድላት ሞክሮ እንዳመለጠ እንዲሁም ደግሞ ኢ ሜይል የተላከላትን የግድያ ማስፈራሪያ ኮፒ ሰጠችው።
ዴሪክ ዊሊያምስ ጆንሰን የተባለው መርማሪ ፖሊስ እሷ ላይ በደረሱ ነገሮች
ላይ ለምን አትኩሮት እንዳልሰጠበት ሊገባው አልቻለም። በተለይ ደግሞ
የተደረገባትን የግድያ ሙከራ እና ምርመራ የሚያደርግበትን ሁለት የግድያ
ጉዳዮችን ለምን ማያያዝ እንዳልፈለገ ግልፅ ሊሆንለት አልቻለም። ምናልባት
ባልደረባው ጉድማን የማያውቀው ነገርን ጆንሰን ያውቅ ይሆን እንዴ? እነዚህን እና መሰል ጥያቄዎቹን በማስታወሻ ደብተሩ ላይ ከትቦ አስቀመጠ።
በመቀጠልም ኒኪ ዋነኛ ጉዳይ ነው ብላ ያሰበችውን የባሏን ውሽማ (ጣውንቷን) ጉዳይ መናገር ስትጀምር በጥሞና ማዳመጥ ጀመረ::
ኒኪ ስለ ጣውንቷ እየነገረችው ያለችው ነገር ሆድ የሚቆርጥ ቢሆንም እሱ ግን እሷ አንድ የደበቀችኝ ነገር አለ ብሎ ስላመነ ሆዱን ሊቆርጠው አልቻለም። አልያም ደግሞ ኒኪ ስለ ነገሩ ብዙ አታውቅም ብሎ እያሰበ ነበር
ሲያዳምጣት የነበረው።
ኒኪ እንደነገረችው ከሆነ ስለ ባሏ እና ስለ ጣውንቷ ለመጀመሪያ ጊዜ ለማወቅ የበቃችው ባሏ 405ኛው ጎዳና ላይ የመኪና አደጋ ደርሶበት ከተደወለላት በኋላ ነበር። እዚያም ስትደርስ ባሏ ዶውግ መኪናው ውስጥ ብቻውን እንዳልነበር ተረዳች።
“አብራው ያለችውን ሴት አውቃት እንደሆነ ጠየቁኝ፡፡ እኔም ሴትየዋን ማን እንደሆነች እንደማላውቅ መለስኩላቸው። በወቅቱ እኔ ያሰብኩት እሷ ታካሚው ወይንም ደግሞ የሥራ ባልደረባው ሆና ምናልባት በአጋጣሚ ሊፍት የሰጣት ሴት አድርጌ ነበር ያሰብኳት። ከጥቂት ቀናት ኋላ ግን
እውነቱን ለማወቅ በቃሁ። ጉዳዩን የሰማሁት ሁለት ፖሊሶች ሲያወሩ
በነበሩበት ጊዜ ላይ ነበር። ዶውግ ይሰራበት የነበረ ሆስፒታል ውስጥ
ከዶውግ ጋር አብረው የሚሠሩ ሰዎችን በሚጠይቁባት ጊዜ ሴትየዋ የዶውግ
ፍቅረኛ እንደሆነች ተናገሩ። ጉዳዩን ስሰማ መጀመሪያ አላመንኩኝም ነበር፡፡
ደግሞም እስከ አሁን ነገሩ ምንም አይነት ስሜት ሳይሰጠኝ ነው የቆየብኝ።
ለማንኛውም በጉዳዩ ዙሪያ ጓደኛውን ሀዶንን ስጠይቀው ግን የሰማሁት ነገር
እውነት እንደሆነ አመነልኝ። በጣም ነበር ልቤ የተሰበረው። ስለ ጉዳዩ
በዝርዝር እንዲነግረኝ ሀዶንን ብለምነውም ከዚህ በላይ ምንም እንደማያውቅ መለሰልኝ።” አለችው ኒኪ፡፡
“እና አመንሽው?”
“አንተ በእኔ ቦታ ብትሆን ታምነው ነበር?” ብላ ኒኪ ጠየቀችው እና በመቀጠልም
“እሱ እና ዶውግ የልብ ጓደኛማቾች ናቸው:: ምናልባት ለእኔ ጉዳዩን በዝርዝር መግለፅ ያልፈለገው እኔ በጣም እንዳልጎዳ ወይንም ደግሞ የጓደኛውን ሚስጥር ለመጠበቅ አስቦ ሊሆን ይችላል ብዬ አምናለሁ። ሀዶን እንደፈለገ አስቦ ጉዳዩን ቢደብቀኝም ግን እኔ በጉዳዩ ላይ መልስ እፈልጋለሁ። ሚ/ር ዊሊያምስ ስለ ጣውንቴ የማውቀው ነገር ቢኖር ሩሲያዊ መሆኗን እና ስሟም ላንከ እንደሚባል ብቻ ነው።”
“ስለ እሷ ምን ምን ነገሮችን ለማወቅ ነው የምትፈልጊው?” ብሎ ዊሊያምስ ጠየቃት፡፡
“ሁሉንም ነገሮች” ብላ ኒኪ አይኗ በቁጣ በራ እና “ስለ እሷ እያንዳንዱን ነገሮች ማወቅ እፈልጋለሁ:: ማን እንደሆነች፣ ለምን ያህል ጊዜ አብረው እንደቆዩ፣ እንዴት እንደተገናኙ፣ የት እንደተገናኙ ሁሉ ማወቅ እፈልጋለሁ።
በየምን ያህል ጊዜያቶች ርቀትስ አብረው ይተኙ እንደነበር፣ የት ቦታ አብረው ይተኙ እንደነበር እና ለምን እሱ እንደዚህ ሊያደርግ እንደቻለም ጭምር ማወቅ እፈልጋለሁ:: ለምን ግን? አየህ እኛ በህይወታችን ደስተኞች ነበርን። ሌላ ሰው እኮ አያስፈልገውም ነበር! እውነት ፍቅራችን ሌሎችን የሚያስቀና ነበር እኮ!” ብላ ከቁጥጥር ውጪ በሆነ ከፍተኛ የንዴት ስሜት ውስጥ ሆና ስታወራው ዴሪክ ዊሊያምስ ዝም ብሎ ያስተውላት ጀመረ።
ስለ ሊዛ እና ትሬይ በመኪና ተገጭታ እንድትሞት ስለተሞከረባት ሁኔታ እና ስለመርማሪ ፖሊሶቹ ስታወራው ራሷን ገዝታ ምንም የስሜት ለውጥ ሳታሳይ ነበር፡፡ ስለ ሟች ባሏ እና ውሽማው
ስታወራው ግን የተረጋጋው ስሜቷ ሙሉ በሙሉ ተለወጠ። የማይበርድ
ሀዘን፣ መከዳት ስሜት እና በጣም ሀይለኛ የንዴት ስሜት ውስጥ ሆና ነበር
ያወራችው።
ይህቺ ሴት ሁለት አይነት ገፅታ ነው ያላት አለ በሃሳቡ፡፡
የመጀመሪያዋ ኒኪ ስሜቶቿን መቆጣጠር የምትችለዋ ናት፡፡ ሁለተኛው ደግሞ በፍፁም ስሜቷን መቆጣጠር የማትችለዋ ኒኪ ናት።
አንደኛዋ ኒኪ በተጨባጩ እውነተኛው ዓለም ውስጥ የምትኖረዋ ስትሆን
ሌላኛዋ ግን በቅዠት ዓለም ውስጥ ጥገኛ የሆነችዋ ኒኪ ናት፡፡
አንደኛዋ ኒኪ እውነት የምትናገረዋ ስትሆን ሌላኛዋ ኒኪ ግን ሰዎችን
እና እራሷን ጭምር የምትዋሸዋ ናት።
ሌላው
“አውቃለው ግን ደንታ የለኝም” ብላ ኒኪ ኮስተር ብላ መልሳለት በመቀጠልም
“ምን መሰለህ እውነታው ሚ/ር ዊሊያምስ? ፖሊሶቹን አላምናቸውም”
አለችው። ይህንን ከእሷ የሰማው ዴሪክ ዊሊያምስም ተነስቶ ቢጨብጣት እና
እኔም አላምናቸውም ቢላት ደስ ባለው ነበር፡፡
“እኔን ግን ታምኚኛለሽ አይደል?” ፈገግ ብሎ ጠየቃት፡፡
“ባላምንብህ ለምን ብዬ ነው የጠየቅከውን ሳልከራከርህ የምከፍልህ” ብላ ኒኪ በፈገግታ መለሰችለት፡፡
“ልክ ነሽ” ብሎ ዊሊያምስ ፈገግ አለ እና “እሺ ይሄንን ብራንዶን የተባለ ልጅን ለመጨረሻ ጊዜ ያገኘሺው መቼ ነው?” ብሎ ጠየቃት፡፡
“ሁ ረዥም ጊዜ አልፎታል ካገኘሁት፡፡ ዓመት አይሆነውም ብለህ ነው? አዎን ከቦስተን ደውሎልኝ ነበር፡፡ አደንዛዥ ዕፅን በድጋሚ መጠቀም ጀምሮ ነበር። በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ነበር ወደ እኔ የደወለው” ብላ ኒኪ መለሰችለት፡፡
“ብራንዶን ሞቷል ብለሽ ታስቢያለሽ?” ብሎ ዊሊያምስ ጠየቃት፡፡
ኒኪም ትከሻዋን ከሰበቀች በኋላ “ሊሞት ይችላል። ግን ስለ እሱ እርግጠኛ ሆኜ ልነግርህ አልችልም”
“እሺ አሁን ደግሞ በግድያው ዙሪያ ላይ ምርመራውን ስለሚያደርጉት
ፖሊሶች ንገሪኝ እስቲ?” አላት፡፡
ኒኪ በረዥሙ አየር ስባ ከተቀመጠች በኋላ መርማሪ ፖሊስ ሚክ ጆንስን ለእሷ ጥሩ አመለካከት እንደሌለው እና እሷንም እንደወንጀለኛ እየቆጠራት እንደሆነ ከነገረችው በኋላ “ባይገርምህ እኔን ገጭቶ ለማምለጥ ሙከራ ስላደረገው ላንድክሩዘር መኪና እና ስላዳነኝ ቀዩ የስፖርት መኪና ሹፌር ሁሉ ፈጥሬ እያወራሁት እንዳለ አምኖ ነው በቁጣ እየወነጀለ ያወራኝ፡፡ ባልደረባው መርማሪ ፖሊስ ሉው ጉድማን ግን ምክንያታዊ ሰው ይመስለኛል” ብላ የጉድማንን ስም ስትጠራ የኒኪ ፊት በፈገግታ ሲፈካ ዴሪክ
ዊሊያምስ ተመለከተ፡፡ “ብቻ እሱ ይለያል” አለችው፡፡
“እሱ በምን መልኩ ነው ይለያል ብለሽ ለመናገር የቻልሽው?”
“እያንዳንዱ ነገሩ። ትሁት ነው፤ ጠንካራ ሠራተኛ ነው፤ የተማረ እና ግልፅ ነገር ነው” ብላ ኒኪ መለሰችላት። እንደዚህ ሆኖም ግን እኮ የምርመራ ጉዳያቸውን ከጫፍ አላደረሰም” ብሎ ዊሊያምስ አሳሰባት፡፡
“ይሆናል” ብላ ኒኪ ቅር እያላት ዊሊያምስ ባነሳው ሀሳብ ተስማማች እና “እርግጥ ነው መዘግየት ይታይበታል፡፡ እሱ እንደነገረኝ ከሆነ ሊዛ ፍላንገን ሊገድል የመጣው ነፍሰ ገዳይ በስህተት እኔን መስላው ነው ሊገድላት የቻለው። ምክንያቱም በወቅቱ እሷ የእኔን የዝናብ ኮት አድርጋ ነበር። ምንም እንኳን እንደ እሷ በጣም ቆንጆ ባልሆንም ቁመታችን
ተመሳሳይ ስለነበረ ነፍሰ ገዳዩ እኔኸ መስዬው እሷን እንደገደላት ግምቱን
አስቀምጦልኛል።”
“ሊያስኬድ ይችላል” ብሎም ዴሪክፀ ዊሊያምስ መለሰላት።
በመቀጠልም ኒኪ ከመኝታ ክፍሏ ውስጥ ስለተሰረቀው ፎቶግራፍ ነገረችው። አስከትላም ጥቁር ላንድሮቨር ገጭቶ ሊገድላት ሞክሮ እንዳመለጠ እንዲሁም ደግሞ ኢ ሜይል የተላከላትን የግድያ ማስፈራሪያ ኮፒ ሰጠችው።
ዴሪክ ዊሊያምስ ጆንሰን የተባለው መርማሪ ፖሊስ እሷ ላይ በደረሱ ነገሮች
ላይ ለምን አትኩሮት እንዳልሰጠበት ሊገባው አልቻለም። በተለይ ደግሞ
የተደረገባትን የግድያ ሙከራ እና ምርመራ የሚያደርግበትን ሁለት የግድያ
ጉዳዮችን ለምን ማያያዝ እንዳልፈለገ ግልፅ ሊሆንለት አልቻለም። ምናልባት
ባልደረባው ጉድማን የማያውቀው ነገርን ጆንሰን ያውቅ ይሆን እንዴ? እነዚህን እና መሰል ጥያቄዎቹን በማስታወሻ ደብተሩ ላይ ከትቦ አስቀመጠ።
በመቀጠልም ኒኪ ዋነኛ ጉዳይ ነው ብላ ያሰበችውን የባሏን ውሽማ (ጣውንቷን) ጉዳይ መናገር ስትጀምር በጥሞና ማዳመጥ ጀመረ::
ኒኪ ስለ ጣውንቷ እየነገረችው ያለችው ነገር ሆድ የሚቆርጥ ቢሆንም እሱ ግን እሷ አንድ የደበቀችኝ ነገር አለ ብሎ ስላመነ ሆዱን ሊቆርጠው አልቻለም። አልያም ደግሞ ኒኪ ስለ ነገሩ ብዙ አታውቅም ብሎ እያሰበ ነበር
ሲያዳምጣት የነበረው።
ኒኪ እንደነገረችው ከሆነ ስለ ባሏ እና ስለ ጣውንቷ ለመጀመሪያ ጊዜ ለማወቅ የበቃችው ባሏ 405ኛው ጎዳና ላይ የመኪና አደጋ ደርሶበት ከተደወለላት በኋላ ነበር። እዚያም ስትደርስ ባሏ ዶውግ መኪናው ውስጥ ብቻውን እንዳልነበር ተረዳች።
“አብራው ያለችውን ሴት አውቃት እንደሆነ ጠየቁኝ፡፡ እኔም ሴትየዋን ማን እንደሆነች እንደማላውቅ መለስኩላቸው። በወቅቱ እኔ ያሰብኩት እሷ ታካሚው ወይንም ደግሞ የሥራ ባልደረባው ሆና ምናልባት በአጋጣሚ ሊፍት የሰጣት ሴት አድርጌ ነበር ያሰብኳት። ከጥቂት ቀናት ኋላ ግን
እውነቱን ለማወቅ በቃሁ። ጉዳዩን የሰማሁት ሁለት ፖሊሶች ሲያወሩ
በነበሩበት ጊዜ ላይ ነበር። ዶውግ ይሰራበት የነበረ ሆስፒታል ውስጥ
ከዶውግ ጋር አብረው የሚሠሩ ሰዎችን በሚጠይቁባት ጊዜ ሴትየዋ የዶውግ
ፍቅረኛ እንደሆነች ተናገሩ። ጉዳዩን ስሰማ መጀመሪያ አላመንኩኝም ነበር፡፡
ደግሞም እስከ አሁን ነገሩ ምንም አይነት ስሜት ሳይሰጠኝ ነው የቆየብኝ።
ለማንኛውም በጉዳዩ ዙሪያ ጓደኛውን ሀዶንን ስጠይቀው ግን የሰማሁት ነገር
እውነት እንደሆነ አመነልኝ። በጣም ነበር ልቤ የተሰበረው። ስለ ጉዳዩ
በዝርዝር እንዲነግረኝ ሀዶንን ብለምነውም ከዚህ በላይ ምንም እንደማያውቅ መለሰልኝ።” አለችው ኒኪ፡፡
“እና አመንሽው?”
“አንተ በእኔ ቦታ ብትሆን ታምነው ነበር?” ብላ ኒኪ ጠየቀችው እና በመቀጠልም
“እሱ እና ዶውግ የልብ ጓደኛማቾች ናቸው:: ምናልባት ለእኔ ጉዳዩን በዝርዝር መግለፅ ያልፈለገው እኔ በጣም እንዳልጎዳ ወይንም ደግሞ የጓደኛውን ሚስጥር ለመጠበቅ አስቦ ሊሆን ይችላል ብዬ አምናለሁ። ሀዶን እንደፈለገ አስቦ ጉዳዩን ቢደብቀኝም ግን እኔ በጉዳዩ ላይ መልስ እፈልጋለሁ። ሚ/ር ዊሊያምስ ስለ ጣውንቴ የማውቀው ነገር ቢኖር ሩሲያዊ መሆኗን እና ስሟም ላንከ እንደሚባል ብቻ ነው።”
“ስለ እሷ ምን ምን ነገሮችን ለማወቅ ነው የምትፈልጊው?” ብሎ ዊሊያምስ ጠየቃት፡፡
“ሁሉንም ነገሮች” ብላ ኒኪ አይኗ በቁጣ በራ እና “ስለ እሷ እያንዳንዱን ነገሮች ማወቅ እፈልጋለሁ:: ማን እንደሆነች፣ ለምን ያህል ጊዜ አብረው እንደቆዩ፣ እንዴት እንደተገናኙ፣ የት እንደተገናኙ ሁሉ ማወቅ እፈልጋለሁ።
በየምን ያህል ጊዜያቶች ርቀትስ አብረው ይተኙ እንደነበር፣ የት ቦታ አብረው ይተኙ እንደነበር እና ለምን እሱ እንደዚህ ሊያደርግ እንደቻለም ጭምር ማወቅ እፈልጋለሁ:: ለምን ግን? አየህ እኛ በህይወታችን ደስተኞች ነበርን። ሌላ ሰው እኮ አያስፈልገውም ነበር! እውነት ፍቅራችን ሌሎችን የሚያስቀና ነበር እኮ!” ብላ ከቁጥጥር ውጪ በሆነ ከፍተኛ የንዴት ስሜት ውስጥ ሆና ስታወራው ዴሪክ ዊሊያምስ ዝም ብሎ ያስተውላት ጀመረ።
ስለ ሊዛ እና ትሬይ በመኪና ተገጭታ እንድትሞት ስለተሞከረባት ሁኔታ እና ስለመርማሪ ፖሊሶቹ ስታወራው ራሷን ገዝታ ምንም የስሜት ለውጥ ሳታሳይ ነበር፡፡ ስለ ሟች ባሏ እና ውሽማው
ስታወራው ግን የተረጋጋው ስሜቷ ሙሉ በሙሉ ተለወጠ። የማይበርድ
ሀዘን፣ መከዳት ስሜት እና በጣም ሀይለኛ የንዴት ስሜት ውስጥ ሆና ነበር
ያወራችው።
ይህቺ ሴት ሁለት አይነት ገፅታ ነው ያላት አለ በሃሳቡ፡፡
የመጀመሪያዋ ኒኪ ስሜቶቿን መቆጣጠር የምትችለዋ ናት፡፡ ሁለተኛው ደግሞ በፍፁም ስሜቷን መቆጣጠር የማትችለዋ ኒኪ ናት።
አንደኛዋ ኒኪ በተጨባጩ እውነተኛው ዓለም ውስጥ የምትኖረዋ ስትሆን
ሌላኛዋ ግን በቅዠት ዓለም ውስጥ ጥገኛ የሆነችዋ ኒኪ ናት፡፡
አንደኛዋ ኒኪ እውነት የምትናገረዋ ስትሆን ሌላኛዋ ኒኪ ግን ሰዎችን
እና እራሷን ጭምር የምትዋሸዋ ናት።
ሌላው
👍2🔥1
በጣም ያስገረመው ነገር ቢኖር ህይወቷ አደጋ ላይ ሆኖ ሰዎች ሊገድሏት እያሳደዷት ባሉበት ወቅት ላይ ሆና ስለ ባሏ ውሽማ ማወቅን ቅድሚያ ሰጥታ መንቀሳቀሷ ነው። የሆነ ያልነገረችኝ ነገር ይኖር ይሆን? ስለ ጣውንቷ ሌንካ የደበቀችው ነገር አለ? ምናልባትም ስለ ጣውንቷ ሌንካ ለማወቅ ያላት የቀን ተቀን እና የማያቋርጠው ጥያቄዋ ይሆን ሞትን እንኳን እንዳትፈራ ያደረጋት? አለ አይደል በባሏ ህይወት ማለፍ መሰቃየቷ
ሳያንሳት በእሱ መከዳቷ ህይወትን እንድትፀየፈው አድርጓት ይሆናል።
ከዚያን ጊዜ በኋላ እንግዲህ ኒኪ ሮበርትሰን ምንም ነገር አያስፈራትምን?
ዊሊያምስ ከህይወት ተሞክሮ አንድ ነገር ተምሯል። እሱም “በህይወት ምንም ነገር ካልቀራቸው ሰዎች የበለጠ በጣም አደገኛ እና አስፈሪ ሰዎች ያለመኖራቸውን ነው::”
ቢሮው ውስጥ ቁጭ ብሎ ስለ ኒኪ ማስታወሻ እየፃፈ አንድ ሰዓት ያህል
አሳለፈ። አሁን ከረፋዱ አምስት ተኩል ነው የምሳ ሰዓት ደርሷል። ያም ቢሆን ግን ዴሪክ ዊሊያምስ መቼም ለሆዱ ቅድሚያ ሰጥቶ አያውቅም እና የምሳ ሰዓትን ችላ አለው:: ስለሆነም ኒኪ ሮበርትስ የሰጠችውን የታሸገ ኤንቨሎፕ ከፍቶ መረጃዎችን መመልከት ጀመረ፡፡
ጠዋት ቁርስ ላይ ከነገረችው መረጃዎች ውስጥ የትኞቹን እዚህ ኤንቨሎፕ ውስጥ ማካተት አለማካተቷንም ለማወቅ ጓጓ። ስለ ብራንዶን የነገረችው ነገር እዚህ ውስጥ የለም፡፡ ስለዚህ ኒኪ እሱን ከፖሊሶቹ በላይ እንዳመነችው ገባው። ይህም ቢሆን ግን ማንኛዎቹም የእሱ ደምበኞች ሙሉ አንድም እውነታቸውን
ሳያስቀሩ ነግረውት እንደማያውቁ ከበፊት
ተሞክሮዎቹ ይረዳል።
ከኤንቨሎፑ ውስጥ አንደኛውን ወረቀት ስቦ ሲያወጣም ልቡ ላይ የሆነ
ስሜት ተሰማው። የተሰማው ነገር ጭንቀት፣ የምግብ አለመፈጨት ስሜት
ወይንም ደግሞ ቃር አልነበረም። አዎን እሱ አሁን ላይ የሚሰማው የደስታ
ስሜት ብቻ ነው። በአንድ ሌሊት ዕድሉ የተለወጠም መሰለው፡፡ አዲስ የምርመራ ጉዳይ እና አዲስ ተግዳሮትን ለማግኘት በቅቷል።
የድሮው ዴሪክ ዊሊያምስ ተመልሷል፡፡
ለረዥም ጊዜ በዝምታ ውስጥ ሆኖ የኒኪን ፋይሎች ከኤንቨሎፕ ውስጥ
እያወጣ አነበባቸው። ደግሞም ደጋግሞም አነበባቸው። ደቂቃዎች ወደ
ስዓቶች ተለወጡ። እሱ ከሚፈልገው ቦታ የጉዳዩን ምርመራ ሀ ብሎ መጀመር ይችላል።
መጨረሻ ላይ ግን ኒኪ በፅሁፍም ሆነ በቃል ከገለፀቻቸው ነገሮች ውስጥ
አንድ ስም ወደ አዕምሮው መጣ፡፡ እነዚህ ሁለት ግድያዎች የተፈፀሙበት ሂደት እና ሌሎች ነገሮችም ከዚህ በፊት ወዳከናወነው የግል ምርመራ ጉዳይ
ወደ ኋላ መለሰው።
አዕምሮውም በግምት ወደ ዛሬ አሥር ዓመት ጉዳይ መለሰው።......
✨ይቀጥላል✨
ሳያንሳት በእሱ መከዳቷ ህይወትን እንድትፀየፈው አድርጓት ይሆናል።
ከዚያን ጊዜ በኋላ እንግዲህ ኒኪ ሮበርትሰን ምንም ነገር አያስፈራትምን?
ዊሊያምስ ከህይወት ተሞክሮ አንድ ነገር ተምሯል። እሱም “በህይወት ምንም ነገር ካልቀራቸው ሰዎች የበለጠ በጣም አደገኛ እና አስፈሪ ሰዎች ያለመኖራቸውን ነው::”
ቢሮው ውስጥ ቁጭ ብሎ ስለ ኒኪ ማስታወሻ እየፃፈ አንድ ሰዓት ያህል
አሳለፈ። አሁን ከረፋዱ አምስት ተኩል ነው የምሳ ሰዓት ደርሷል። ያም ቢሆን ግን ዴሪክ ዊሊያምስ መቼም ለሆዱ ቅድሚያ ሰጥቶ አያውቅም እና የምሳ ሰዓትን ችላ አለው:: ስለሆነም ኒኪ ሮበርትስ የሰጠችውን የታሸገ ኤንቨሎፕ ከፍቶ መረጃዎችን መመልከት ጀመረ፡፡
ጠዋት ቁርስ ላይ ከነገረችው መረጃዎች ውስጥ የትኞቹን እዚህ ኤንቨሎፕ ውስጥ ማካተት አለማካተቷንም ለማወቅ ጓጓ። ስለ ብራንዶን የነገረችው ነገር እዚህ ውስጥ የለም፡፡ ስለዚህ ኒኪ እሱን ከፖሊሶቹ በላይ እንዳመነችው ገባው። ይህም ቢሆን ግን ማንኛዎቹም የእሱ ደምበኞች ሙሉ አንድም እውነታቸውን
ሳያስቀሩ ነግረውት እንደማያውቁ ከበፊት
ተሞክሮዎቹ ይረዳል።
ከኤንቨሎፑ ውስጥ አንደኛውን ወረቀት ስቦ ሲያወጣም ልቡ ላይ የሆነ
ስሜት ተሰማው። የተሰማው ነገር ጭንቀት፣ የምግብ አለመፈጨት ስሜት
ወይንም ደግሞ ቃር አልነበረም። አዎን እሱ አሁን ላይ የሚሰማው የደስታ
ስሜት ብቻ ነው። በአንድ ሌሊት ዕድሉ የተለወጠም መሰለው፡፡ አዲስ የምርመራ ጉዳይ እና አዲስ ተግዳሮትን ለማግኘት በቅቷል።
የድሮው ዴሪክ ዊሊያምስ ተመልሷል፡፡
ለረዥም ጊዜ በዝምታ ውስጥ ሆኖ የኒኪን ፋይሎች ከኤንቨሎፕ ውስጥ
እያወጣ አነበባቸው። ደግሞም ደጋግሞም አነበባቸው። ደቂቃዎች ወደ
ስዓቶች ተለወጡ። እሱ ከሚፈልገው ቦታ የጉዳዩን ምርመራ ሀ ብሎ መጀመር ይችላል።
መጨረሻ ላይ ግን ኒኪ በፅሁፍም ሆነ በቃል ከገለፀቻቸው ነገሮች ውስጥ
አንድ ስም ወደ አዕምሮው መጣ፡፡ እነዚህ ሁለት ግድያዎች የተፈፀሙበት ሂደት እና ሌሎች ነገሮችም ከዚህ በፊት ወዳከናወነው የግል ምርመራ ጉዳይ
ወደ ኋላ መለሰው።
አዕምሮውም በግምት ወደ ዛሬ አሥር ዓመት ጉዳይ መለሰው።......
✨ይቀጥላል✨
🔥1
#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....ናትናኤል ለጥያቄው መልስ ሲያገኝ ይበልጥ ተበሳጨ፡፡ ለዚህ ቀላል ጥያቄ፣ ለዚህ ቀላል መልስ ይህን ያህል ከተቸገረ እንግዲያው ማስተዋል ቀንሷል ማለት ነው ከሚገባው በላይ ተወናብዷል ማለት ነው፡፡ ፈርቷል ማለት ነው፡፡
እራሱን ገሰጸወ፡፡
ረጋ ማለት አለበት፡፡ አለበለዚያ በማይረባ ስህተት እራሱን አጋልጦ ይሰጣል፡፡
ስሟን እስካወቀ፤ የስልክ ቁጥሯን እስካወቀ፤ የአባቷንና የአያቷን ስም ከማንኛውም የስልክ ደብተር ላይ በቀላሉ ያገኘዋል፡፡
ሌሊቱን በሙሉ በሃሳብ ሲታመስ ሳያሸልበው ፀሐይ ሥፍራዋን
ተረከበች::
ናትናኤል ከአልጋው ተነስቶ ማታ አለቅልቆና በእርጥብ መሃረቡ
ጠራርጎ ከግርጌ ካለ ወንበር ላይ ያሰጣቸውን ሸሚዙንና ኮቱን አንስቶ
ለባበሰና ወደ መታጠቢያ ቤት ገባ፡፡ በተቻለው መጠን ረጋ ብሎ ተጣጥቦ
ያለፈውን ሌሊት አሻራ ሙልጭ አድርጎ ካፀዳ በኋላ ወደ ሆቴሉ አዳራሽ ብቅ
አለ፡፡
ጥግ ላይ ተቀምጦ ሁለት ስኒ ቡና ጠጣና ፈጠን ብሎ ከሆቴሉ ወጣ፡፡ ሌላቱን ያለእንቅልፍ ቢያሳልፈውም የድካም ስሜት አልተሰማውም፡፡ምናልባት ድንጋጤው ይሆናል፧ ምናልባት ፍርሃት፣ ምናልባት ሥጋት፡፡
ደሙ በሰውነቱ ውስጥ ሲሽቀዳደምና ሲራወጥ ለራሱ ይሰማዋል፡፡ መፍጠኝና
መሮጥ አለበት!
ታክሲ ተሳፈረና ወደ መርካቶ ሸሸ፡፡
መርካቶ ባህር ነው ውቅያኖስ፤ መርካቶ ጫካ ነው ደን፡፡መርካቶ ቤቱ ነው የዘውድዬ፡፡
መሀል መርካቶ ከታክሲ እንደወረደ ወደ አንድ ቡና ቤት ገባ፡፡ገንዘብ ተቀባይዋን ተጠግቶ ሠላምታ ከሰጣት በኋሳ የስልክ ማውጫ ጠየቃት፡፡
“ጩኒ ቁልፍ፡፡” አለች ረጅም ወንበር ላይ የተቀመጠችው ወጣት ሴት ወደኋላ ዞራ፡፡
“ በእድሜ የሚመጣጠናት ወንድ ልጅ በቀጭን ሰንሰለት ውስጥ የተሰገሰጉ አስር የሚሆን ቁልፎች አቀበላት፡፡ ከቁልፎቹ ውስጥ አንዷን መርጣ አወጣችና አጠገቧ ያለ መሳቢያ ስባ የስልኩን ደብተር አውጥታ
አቀበለችው::
"እግዜር ይስጥልኝ” አላት ማውጫውን ተቀብሏት እየከፈተው፡፡
'የምሥራች ይልማ መጀመሪያ የምሥራችን ስም ፈለገ፡፡ በርካታ የምሥራች ይልማዎች የተደረደሩትን ገፅ እንዳገኘ የስልክ ቁጥሯን ፈለገው:: ቁጥሩን እንዳገኘ ወደኋላ ተመልሶ በትይዩ የተፃፈውን የምሥራችን ስም እስከ አያቷ ስም አነበበው የምሥራች ይልማ ገዛኽኝ::
“እቶ ይልማ ገዛኸኝ ድጋሚ የስልክ ማውጫውን እያገለባበጠ
ይፈልግ ጀመር አቶ ያልማ ገዛኸኝ... ይ.… ይ. ይ.. ያልማ አዳሙ... ይልማ መብራቱ
ይልማ ገብረማርያም…ያልማ ገዛኽኝ
የስልክ ቁጥሩን በወረቀት ላይ ገለበጠና የቡና ቤቱን ገንዘብ ተቀባይ አመስግኖ ወጣ፡፡ እዚያው አካባቢ የሕዝብ ስልክ ፈልጎ ኣቶ ይልማ ገዛኸኝ መኖሪያ ቤት ደወለ፡፡“
ከቤት” አለው ቀጠን ያለ የሴት ድምፅ፡፡
“እባኮት አቶ ይልማን ነበር”
“ሥራ ናቸው” አለች ሴትየዋ በተሰላቸ ድምዕ::
“እባኮት ችግር ገጥሞኝ ነው የሥራ ቦታቸውን ስልክ ቢሰጡኝ፡፡
“የሱቁን ነው?”
“አዎ ላገኛቸው የምችልበትን ቦታ፡፡”
ነገረችው:: ቀልጠፍ ብሎ ቁጥሩን ጻፍ ጻፍ አደረገና አመስግኗት ስልኩን ዘጋ:: ወዲያው የሰጠችውን ቁጥር ደወለ፡፡
ሃሎ” አለ ውፍረት የደፈነወ፣ ስጋ የዘጋው፣ እርስ በእርስ የሚተሻሽ ድምፅ::
“እባኮት አቶ ያልማ ይኖራሉ?”
“ነኝ:: ማን ልበል?”
“እንደምን ዋላ፡፡ የምሥራች ነበረች የላከችኝ..." ናትናኤል የሰውየውን ስሜት ለማጥናት ለአንድ አፍታ ዝም አለ፡፡
“ማን አሉኝ?” አለ ሰውየው መልሰው፡፡
“የምሥራች… የምሥራች ይልማ፡፡”
“ከየት ነው? ማንን ነው የሚፈልጉት?” ሰውየው ግራ የተጋቡ መሰሉ፡፡
“የምሥራች... የምሥራች የእርሶ ልጅ::”
“የማን ልጅ? ” ሰውየው ያበልጥ ተደነጋገራቸው፡፡
““ካዛንቺስ ሆቴል ያላት የእርሶ ልጅ::የምሥራች ይልማ ባለሆቴሏ...
“የምን ሆቴል ነው የሚሉኝ?”
ይቐርታ ጠይቋቸው ስልኩን ዘጋ፡፡
ሌላ ይልማ ገዛኽኝ በአዲስ አበባ ስልክ ማውጫ ደብተር ውስጥ የተመዘገበ የለም፡፡ ያለው አማራጭ ወደ ድሬዳዋ መንጎድ ብቻ ነው፡፡ድሬዳዋን አያውቃትም:: እዚያም ሄዶ መቸገሩ የማይቀር ነው፡፡ ግን የተሻለ
ምርጫ የለም::
መፍጠን አለበት፡፡ ምንም ጠባብ ቢሆን በተከፈተለት በር ሁሉ መሮጥ አለበት፡፡
ወደ ካልቨርት መጠጋት አለበት::
ዝግጅቱን ለማጠናቀቅ ወደ ባቡር ጣቢያ ሄዶ በማግስቱ ምሽት ላይ ወደ ድሬዳዋ በሚሄድ ባቡር ላይ የሁለተኛ ማዕረግ ትኬት ከቆረጠ በኋላ አውቶቡስ ተራ ወደ ዘውዲቱ ቤት ወደ ጎሬው በረረ፡፡
ምሳውን ከዘውዲቱ ጋር ከበላ በኋላ አሰዓት ወደ ገበያ ወጣ፡፡መርካቶ የዘመን መለወጫ በዓልን መስከረም አንድን ለመቀበል በሚዘገጃጅ ገብያተኛ ተጣባለች፡፡
ወደ ድሬዳዋ ሲሄድ ሊለብስ ያሰበውን ጀለቢያና ሽርጥ ነጠላ ጫማ እንዲሁም አንድ አነስተኛ የሸራ ሻንጣ ገዛ፡፡ አዲስ አበባ እስካለ ድረስ ደግሞ አጥልቆት የሚዘዋወረውን ወራጅ የጋራዥ ቱታና ፊቱን ጥሩ እድርጋ የምትሸፍንለት አንድ የተልፈሰፈሰች ባርኔጣ ጨመረ፡፡መንገድ ላይ ከኣንድ ጋራዥ ገባ ብሎ ለዘበኛወ ሁለት ብር ሰጠና በትንሽ ቆርቆሮ የተቃጠለ ዘያት ይዞ ወደ ጎሬው ሲመለስ ከእንድ ሱቅ ጎብቶ አንድ ጥሩ ሽቶና የሴት
ነጠላ ጫማ ሾመተ:: ከዘውዲቱ ቤት ሲደርስ ባይመሽም ቀኑ ገፍቶ ነበር።
ልብሱን አወላልቆ ዘወዲቱ እልጋ ወስጥ ገብቶ ጥቅልል አለ፡፡ የዘውዲቱን ቤት ተከራይቶ ከገባ ጀምር ለመጀመሪያ ጊዜ ዘውዲቱ፡ አብሯት የሚያድር ደንበኛ አጥታ እንድትመጣ ተመኘ፡፡
ያን ሌሊት በውዲቱ ቀንቷት ደንበኛ አገኘች አልተመለሰችም፡፡አልጋዊ ላይ ብቻዉን ሲገላበጥ ሲያቃዠው አደረ፡፡አንዱን ቅዠት ሳያገባድድ ሌላ ቅዠት እያቋረጠው ያባረረው ውሻ ሳያዘው ጭልጥ ካለ ገደል እየገባ ከገደሉ ወለል ደርሶ አናቱ እንደ እንቁላል ሳይፈርጥ አየር ላይ ጭልፊቶች
ገላውን እየገመጡ አይኖቹን እየጓጎጡት ሲወራጭ አደረ፡፡
ጠዋት በሩ ሲከፈት በርግጎ ሲነሳ ጭንቅላቱን በፋስ ሲወቅረው ተሰማው እራስ ምታት ነፍስ ዘርቶ፡፡
“እንደምን አደርክ?” አለችው ዘውዲቱ ወደ ውስጥ ገብታ በሩን እየዘጋች፡፡ እስካሁን አልተነሳህም? ሁለት ሰዓት አልፏልኮ::” የያዘችውን የላስቲክ ከረጢት ወንበር ላይ ጣል ኣድርጋ ኣልጋው ጫፍ ላይ ቁጭ አለችና ኩንታል ስትሸከም እንዳደረች “
ኡፍ.....ፍ፡!” አለች፡፡ “እንዴ ለምን እራትህን ሳትበላ አደርክ?” አለች ሳይከፈት ያደረውን የምግብ ሳህን ከራስጌ ስታይ ዞራ እየተመለከተችው::
“አላየሁትም ነበር፡፡” አላት ናትናኤል እራቁት ደረቱን እያከከ ዞር ከራስጌ የተቀመጠውን ሳህን እየተመለከተ::
“እና ጾምን አደርክ ማለት ነው? ደግሞ ከትላንት ወዲያ የት ነበር ያደርከው?” ጥያቄ አከታተለችበት፡፡
ሳይመልስላት ከአልጋው ተነስቶ ከወገቡ በላይ ለመለቃለቅ በሩን ከፍቶ ወጣ፡፡ ሰወነቱን ተለቃልቆ ሲመለስ ዘውዲቱ ከራስጌ ያደረውን ሳህን ከፍታ በግራ እጇ ይዛ እየተንጎራደደች በላይ በላዩ ስትጎርስ አገኛት::
“ቡዳ የሆነ ሰውዬ ራቴን ሳያበላኝ ቤቱ ወስዶ እንደቅሪላ ሲያለፋኝ አደረ::” አለች እየሳቀች፡፡ “ላጉርስህ? ”
ራሱን ነቀነቀ፡፡ ናትናኤል ምግብ አላሰኘውም፡፡
“ምን ሆነሃል? ቤት ደህና አይደሉም እንዴ? ”
“ደህና ናቸው እነሱስ...” የጀመረውን አንጠልጥሎ ተወው፡፡
“ታዲያ ምን ሆነሃል? "
“ሰውየው ተያዘ::”
የቱ ሰውዬ?” መንጎራደዷን አቁማ በተቀመጠበት ቁልቁል ተመለከተችው፡፡
“አለቃዬ። የመሥሪያ ቤታችንን ገንዘህ ያጠፋው፡፡”
“አትለኝም!” የያዘችውን የምግብ ሳህን ከራስጌ አስቀምጣ በወጥ የተጨማለቀ እጇን አንከርፋ ኣልጋው ላይ ከጎኑ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
....ናትናኤል ለጥያቄው መልስ ሲያገኝ ይበልጥ ተበሳጨ፡፡ ለዚህ ቀላል ጥያቄ፣ ለዚህ ቀላል መልስ ይህን ያህል ከተቸገረ እንግዲያው ማስተዋል ቀንሷል ማለት ነው ከሚገባው በላይ ተወናብዷል ማለት ነው፡፡ ፈርቷል ማለት ነው፡፡
እራሱን ገሰጸወ፡፡
ረጋ ማለት አለበት፡፡ አለበለዚያ በማይረባ ስህተት እራሱን አጋልጦ ይሰጣል፡፡
ስሟን እስካወቀ፤ የስልክ ቁጥሯን እስካወቀ፤ የአባቷንና የአያቷን ስም ከማንኛውም የስልክ ደብተር ላይ በቀላሉ ያገኘዋል፡፡
ሌሊቱን በሙሉ በሃሳብ ሲታመስ ሳያሸልበው ፀሐይ ሥፍራዋን
ተረከበች::
ናትናኤል ከአልጋው ተነስቶ ማታ አለቅልቆና በእርጥብ መሃረቡ
ጠራርጎ ከግርጌ ካለ ወንበር ላይ ያሰጣቸውን ሸሚዙንና ኮቱን አንስቶ
ለባበሰና ወደ መታጠቢያ ቤት ገባ፡፡ በተቻለው መጠን ረጋ ብሎ ተጣጥቦ
ያለፈውን ሌሊት አሻራ ሙልጭ አድርጎ ካፀዳ በኋላ ወደ ሆቴሉ አዳራሽ ብቅ
አለ፡፡
ጥግ ላይ ተቀምጦ ሁለት ስኒ ቡና ጠጣና ፈጠን ብሎ ከሆቴሉ ወጣ፡፡ ሌላቱን ያለእንቅልፍ ቢያሳልፈውም የድካም ስሜት አልተሰማውም፡፡ምናልባት ድንጋጤው ይሆናል፧ ምናልባት ፍርሃት፣ ምናልባት ሥጋት፡፡
ደሙ በሰውነቱ ውስጥ ሲሽቀዳደምና ሲራወጥ ለራሱ ይሰማዋል፡፡ መፍጠኝና
መሮጥ አለበት!
ታክሲ ተሳፈረና ወደ መርካቶ ሸሸ፡፡
መርካቶ ባህር ነው ውቅያኖስ፤ መርካቶ ጫካ ነው ደን፡፡መርካቶ ቤቱ ነው የዘውድዬ፡፡
መሀል መርካቶ ከታክሲ እንደወረደ ወደ አንድ ቡና ቤት ገባ፡፡ገንዘብ ተቀባይዋን ተጠግቶ ሠላምታ ከሰጣት በኋሳ የስልክ ማውጫ ጠየቃት፡፡
“ጩኒ ቁልፍ፡፡” አለች ረጅም ወንበር ላይ የተቀመጠችው ወጣት ሴት ወደኋላ ዞራ፡፡
“ በእድሜ የሚመጣጠናት ወንድ ልጅ በቀጭን ሰንሰለት ውስጥ የተሰገሰጉ አስር የሚሆን ቁልፎች አቀበላት፡፡ ከቁልፎቹ ውስጥ አንዷን መርጣ አወጣችና አጠገቧ ያለ መሳቢያ ስባ የስልኩን ደብተር አውጥታ
አቀበለችው::
"እግዜር ይስጥልኝ” አላት ማውጫውን ተቀብሏት እየከፈተው፡፡
'የምሥራች ይልማ መጀመሪያ የምሥራችን ስም ፈለገ፡፡ በርካታ የምሥራች ይልማዎች የተደረደሩትን ገፅ እንዳገኘ የስልክ ቁጥሯን ፈለገው:: ቁጥሩን እንዳገኘ ወደኋላ ተመልሶ በትይዩ የተፃፈውን የምሥራችን ስም እስከ አያቷ ስም አነበበው የምሥራች ይልማ ገዛኽኝ::
“እቶ ይልማ ገዛኸኝ ድጋሚ የስልክ ማውጫውን እያገለባበጠ
ይፈልግ ጀመር አቶ ያልማ ገዛኸኝ... ይ.… ይ. ይ.. ያልማ አዳሙ... ይልማ መብራቱ
ይልማ ገብረማርያም…ያልማ ገዛኽኝ
የስልክ ቁጥሩን በወረቀት ላይ ገለበጠና የቡና ቤቱን ገንዘብ ተቀባይ አመስግኖ ወጣ፡፡ እዚያው አካባቢ የሕዝብ ስልክ ፈልጎ ኣቶ ይልማ ገዛኸኝ መኖሪያ ቤት ደወለ፡፡“
ከቤት” አለው ቀጠን ያለ የሴት ድምፅ፡፡
“እባኮት አቶ ይልማን ነበር”
“ሥራ ናቸው” አለች ሴትየዋ በተሰላቸ ድምዕ::
“እባኮት ችግር ገጥሞኝ ነው የሥራ ቦታቸውን ስልክ ቢሰጡኝ፡፡
“የሱቁን ነው?”
“አዎ ላገኛቸው የምችልበትን ቦታ፡፡”
ነገረችው:: ቀልጠፍ ብሎ ቁጥሩን ጻፍ ጻፍ አደረገና አመስግኗት ስልኩን ዘጋ:: ወዲያው የሰጠችውን ቁጥር ደወለ፡፡
ሃሎ” አለ ውፍረት የደፈነወ፣ ስጋ የዘጋው፣ እርስ በእርስ የሚተሻሽ ድምፅ::
“እባኮት አቶ ያልማ ይኖራሉ?”
“ነኝ:: ማን ልበል?”
“እንደምን ዋላ፡፡ የምሥራች ነበረች የላከችኝ..." ናትናኤል የሰውየውን ስሜት ለማጥናት ለአንድ አፍታ ዝም አለ፡፡
“ማን አሉኝ?” አለ ሰውየው መልሰው፡፡
“የምሥራች… የምሥራች ይልማ፡፡”
“ከየት ነው? ማንን ነው የሚፈልጉት?” ሰውየው ግራ የተጋቡ መሰሉ፡፡
“የምሥራች... የምሥራች የእርሶ ልጅ::”
“የማን ልጅ? ” ሰውየው ያበልጥ ተደነጋገራቸው፡፡
““ካዛንቺስ ሆቴል ያላት የእርሶ ልጅ::የምሥራች ይልማ ባለሆቴሏ...
“የምን ሆቴል ነው የሚሉኝ?”
ይቐርታ ጠይቋቸው ስልኩን ዘጋ፡፡
ሌላ ይልማ ገዛኽኝ በአዲስ አበባ ስልክ ማውጫ ደብተር ውስጥ የተመዘገበ የለም፡፡ ያለው አማራጭ ወደ ድሬዳዋ መንጎድ ብቻ ነው፡፡ድሬዳዋን አያውቃትም:: እዚያም ሄዶ መቸገሩ የማይቀር ነው፡፡ ግን የተሻለ
ምርጫ የለም::
መፍጠን አለበት፡፡ ምንም ጠባብ ቢሆን በተከፈተለት በር ሁሉ መሮጥ አለበት፡፡
ወደ ካልቨርት መጠጋት አለበት::
ዝግጅቱን ለማጠናቀቅ ወደ ባቡር ጣቢያ ሄዶ በማግስቱ ምሽት ላይ ወደ ድሬዳዋ በሚሄድ ባቡር ላይ የሁለተኛ ማዕረግ ትኬት ከቆረጠ በኋላ አውቶቡስ ተራ ወደ ዘውዲቱ ቤት ወደ ጎሬው በረረ፡፡
ምሳውን ከዘውዲቱ ጋር ከበላ በኋላ አሰዓት ወደ ገበያ ወጣ፡፡መርካቶ የዘመን መለወጫ በዓልን መስከረም አንድን ለመቀበል በሚዘገጃጅ ገብያተኛ ተጣባለች፡፡
ወደ ድሬዳዋ ሲሄድ ሊለብስ ያሰበውን ጀለቢያና ሽርጥ ነጠላ ጫማ እንዲሁም አንድ አነስተኛ የሸራ ሻንጣ ገዛ፡፡ አዲስ አበባ እስካለ ድረስ ደግሞ አጥልቆት የሚዘዋወረውን ወራጅ የጋራዥ ቱታና ፊቱን ጥሩ እድርጋ የምትሸፍንለት አንድ የተልፈሰፈሰች ባርኔጣ ጨመረ፡፡መንገድ ላይ ከኣንድ ጋራዥ ገባ ብሎ ለዘበኛወ ሁለት ብር ሰጠና በትንሽ ቆርቆሮ የተቃጠለ ዘያት ይዞ ወደ ጎሬው ሲመለስ ከእንድ ሱቅ ጎብቶ አንድ ጥሩ ሽቶና የሴት
ነጠላ ጫማ ሾመተ:: ከዘውዲቱ ቤት ሲደርስ ባይመሽም ቀኑ ገፍቶ ነበር።
ልብሱን አወላልቆ ዘወዲቱ እልጋ ወስጥ ገብቶ ጥቅልል አለ፡፡ የዘውዲቱን ቤት ተከራይቶ ከገባ ጀምር ለመጀመሪያ ጊዜ ዘውዲቱ፡ አብሯት የሚያድር ደንበኛ አጥታ እንድትመጣ ተመኘ፡፡
ያን ሌሊት በውዲቱ ቀንቷት ደንበኛ አገኘች አልተመለሰችም፡፡አልጋዊ ላይ ብቻዉን ሲገላበጥ ሲያቃዠው አደረ፡፡አንዱን ቅዠት ሳያገባድድ ሌላ ቅዠት እያቋረጠው ያባረረው ውሻ ሳያዘው ጭልጥ ካለ ገደል እየገባ ከገደሉ ወለል ደርሶ አናቱ እንደ እንቁላል ሳይፈርጥ አየር ላይ ጭልፊቶች
ገላውን እየገመጡ አይኖቹን እየጓጎጡት ሲወራጭ አደረ፡፡
ጠዋት በሩ ሲከፈት በርግጎ ሲነሳ ጭንቅላቱን በፋስ ሲወቅረው ተሰማው እራስ ምታት ነፍስ ዘርቶ፡፡
“እንደምን አደርክ?” አለችው ዘውዲቱ ወደ ውስጥ ገብታ በሩን እየዘጋች፡፡ እስካሁን አልተነሳህም? ሁለት ሰዓት አልፏልኮ::” የያዘችውን የላስቲክ ከረጢት ወንበር ላይ ጣል ኣድርጋ ኣልጋው ጫፍ ላይ ቁጭ አለችና ኩንታል ስትሸከም እንዳደረች “
ኡፍ.....ፍ፡!” አለች፡፡ “እንዴ ለምን እራትህን ሳትበላ አደርክ?” አለች ሳይከፈት ያደረውን የምግብ ሳህን ከራስጌ ስታይ ዞራ እየተመለከተችው::
“አላየሁትም ነበር፡፡” አላት ናትናኤል እራቁት ደረቱን እያከከ ዞር ከራስጌ የተቀመጠውን ሳህን እየተመለከተ::
“እና ጾምን አደርክ ማለት ነው? ደግሞ ከትላንት ወዲያ የት ነበር ያደርከው?” ጥያቄ አከታተለችበት፡፡
ሳይመልስላት ከአልጋው ተነስቶ ከወገቡ በላይ ለመለቃለቅ በሩን ከፍቶ ወጣ፡፡ ሰወነቱን ተለቃልቆ ሲመለስ ዘውዲቱ ከራስጌ ያደረውን ሳህን ከፍታ በግራ እጇ ይዛ እየተንጎራደደች በላይ በላዩ ስትጎርስ አገኛት::
“ቡዳ የሆነ ሰውዬ ራቴን ሳያበላኝ ቤቱ ወስዶ እንደቅሪላ ሲያለፋኝ አደረ::” አለች እየሳቀች፡፡ “ላጉርስህ? ”
ራሱን ነቀነቀ፡፡ ናትናኤል ምግብ አላሰኘውም፡፡
“ምን ሆነሃል? ቤት ደህና አይደሉም እንዴ? ”
“ደህና ናቸው እነሱስ...” የጀመረውን አንጠልጥሎ ተወው፡፡
“ታዲያ ምን ሆነሃል? "
“ሰውየው ተያዘ::”
የቱ ሰውዬ?” መንጎራደዷን አቁማ በተቀመጠበት ቁልቁል ተመለከተችው፡፡
“አለቃዬ። የመሥሪያ ቤታችንን ገንዘህ ያጠፋው፡፡”
“አትለኝም!” የያዘችውን የምግብ ሳህን ከራስጌ አስቀምጣ በወጥ የተጨማለቀ እጇን አንከርፋ ኣልጋው ላይ ከጎኑ
👍1
ተቀመጠችና አይን አይኑን ትመለክታው ጀመር፡፡ “ውሸትክን ነው!”
ናትናኤል ከዘውዲቱ የሚለይበት ሰዓት እንደደረሰ የተገነዘበው ከአንድ ቀን በፊት ነበር፡፡ የምሥራች “እማዬ ጋ... ድሬዳዋ” ካለችው ወዲያ:: ዘወዲቱን ሊሰናበታት ደግሞ ምክንያት መስጠት አለበት፡፡ ቢሆንም ችግሩ ሁሉ እንደተፈታ አድርጎ መቅረብ የለበትም፡፡ መጪው አይታወቅም፡፡ ማን ያውቃል.. ተመልሶ ወደ አዲስ ኣበባ መምጣትና መሸሸግ ያስፈልገው ይሆናል፡፡ ያን ጊዜ የት ይገባል? ዞሮ መግቢያው መሽሽጊያው ነች ዘወዲቱ፡፡
“አዎ ተያዝ ዘውድዬ እየተመረመረ ነው አሉ፡፡ ግን ገና ነው! ያመነ አይመስለኝም፡፡
እሺ...አለች ለተጨማሪ ወሬ ጓጉታ ድዷ ውስጥ የገባ ምግብ በምላሷ እየጠረገች፡፡
ግን መጥፎ ወሬ ሰማሁ…“
“ምን?'' ቅንድቦቿን አጠበበቻቸው::
“ፖሊሶች አዲስ ኣበባ ውስጥ መደበቄን ደርሰውበታል አሉ፡፡ ያየኝ ሰው ሳይመራብኝ አልቀረም::”
ገብርኤልን.…” ደነገጠች:: “እንዴት አወቅህ? ።
“በየዘመዶቼና በየጓደኞቹ ቤት እየዞሩ ሲያጠያይቁ ነው እሉ የሰነበቱት፡፡” አላት ሃሳብ እንደገባው ሁሉ አይኖቹን ቡዝዝ አድርጎ ለምጻም ግድግዳዋ ላይ ተክሎ፡፡
“አይዞህ፡፡ እዚህ ሊያገኙህ አይችሉም፤ ከቤት ያለመውጣት ነው... ድምፅህን ካጠፋህ…” ታረጋጋው ጀመረች::
“አይ ዘውድዬ…. እኔም ተይዤ ለኣንቺም መዘዝ ከምሆን ከአዲስ አበባ ብወጣ ይሻላል:: እማዬጋ ልሄድ ነው ያሰብኩት::”
“የት ናቸው እናትህ?"- .
“ደብረብርሃን፡፡”
ከሰዓት በኋላ ጀለቢያውን ነጠላ ጫማውን ሌሎቹንም እቃዎቹን
በሸራው ቦርሳ ውስጥ ቀርቅቦ፤ በተቃወለ ጥቁር ዘይት የተጨማለቀ ቱታውን አጥልቆ፣ ልፍስፍስ ባርኔጣውን አድርጎ ተሰናበታት፡፡
“ልክ አይደለሀም፡፡ ይሄን ያህል ጊዜ አብረን ቆይተን ዘመን መለወጫ ሁለት ቀን ሲቀረው ትተኸኝ ትሄዳለህ? በፍጹም ልክ አይደለም፡፡ ምናለበት
ሁለት ቀን ቆይተህ እንቁጣጣሽን አብረን ብናሳልፍ ተለማመጠችው::
“አይሆንም ዘዉድዩ:: ከደረሱብኝ መጥፎ ነው::" አለ ጊዜ ማጥፋት እንደማይገባው ለራሱ እየመከረ፡፡ ዘውድዬ ይሄን ለአንቺ ነው የገዛሁት፡፡” አላት ሽቶውንና ነጠላ ጫማውን እየሰጣት፡፡ “ብድር መመለሴ አይደለም፤ ብድርሽን የምመልሰው ጥሩ ቀን ሲመጣ ነው፡፡ ይሄን ለዘመን መለወጫ ነው የገዛሁልሽ፡፡”
የዘውዲቱ ዓይኖች በእንባ ተሞሉ፡፡ ለስላሳነት ሲያይባት የመጀመሪያ ጊዜው ነበር፡፡ ሁሌ ተናጋሪ ሁሌ ግድ የለሽ ነበረች ዘውዲቱ፡፡አይኖቿ ውስጥ ያቆረዘዘውን እንባ ሲመለከት እሷም ለስላሳ፣ እሷም ሙቅ እንደሆነች ተረዳ፡፡
ዘላ አንገቱ ላይ ተጠመጠመችበት፡፡
ከዘውዲቱ ቤት ሲወጣ ዘጠኝ ሰዓት አልሞላም ነበር፡፡ ወደ ድሬዳዋ የሚጓዘው ባቡር ምሽት ላይ ይነሳል፡፡ ወደ ድሬዳዋ ከመሄዱ በፊት ግን ርብቃ መሥሪያ ቤት ለመደወል ወሰነ::
ርብቃ መሥሪያ ቤት ሲደውል ምህረትን ሲያገኝ ግን ያልጠበቀው ዱብ ዕዳ ጭንቅላቱን መታው የሱ ርብቃ አርግዛለች…የሱ ርብቃ ልጁን በሆዷ ተሸክማ ብቻዋን ትጨነቃለች.… የሱ ርብቃ…
ናትናኤል ወደኋላ ጋለል ካለበት ወንበር ላይ ቀና ኣለና ተቀመጠ፡፡ሰዓቱን ተመለከተ አስራ ኣንድ ተኩል ሊል ነው፡፡ የርብቃን ወንድም በአስራ ሁለት ተኩል ነው የቀጠረው፡፡ አንድ ሰዓት አለው ማለት ነው::
ከተቀመጠበት ተነስቶ ከቡና ቤቱ ወጣ፡፡ ሰማዩ ላይ ያዘበዘበው እርጉዝ ደመና ሌሊቱን ሀይለኛ ዝናብ ሊጥል እንዳሰበ ያስታውቃል፡፡ ለገሃር ታክሲ ይዞ በቸርችል ጎዳና ሽቅብ ወደ ፒያሳ ወደ ርብቃ አፓርታማ አመራ።
መጠንቀቅ አለበት፡፡ በቤቷ አካባቢ የሚያንዣብቡ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ሲገባና ሲወጣ መታየት የለበትም፡፡ አለበለዚያ እሮጦ ከእጃቸው እንደገባላቸው ነው የሚቆጠር፡፡ መጠንቀቅ አለበት፡፡ ቀጥታ ወደ ክፍሏ
ማምራት የለበትም። መሰለል… ዙሪያውን ማጥናትና መጠንቀቅ አለበለዚያ
ለሷም ተጨማሪ ችግር ነው የሚፈጥርባት፡
ርብቃ አፓርትመንት ከመድረሱ በፊት እራቅ ብሎ ከታክሲ ወረደና የስራ ሻንጣውን ትከሻው ላይ አንግቦ ጭንቅላቱ ላይ የደፋትን የጨርቅ ቆብ ወደ ታች ወደ ግንባሩ እየጎተተ በመንገዱ ቁልቁል በእርጋታ ወረደ፡፡ ሰዓቱ ገና ቢሆንም ከዳር እስከ ዳር ያንዣበበው ጥቁር ደመና አካባቢውን የመሸ አስመስሎታል፡፡ ሰዓቱን ተመለከተ፡፡ በአንድ ሰዓት አካባቢ ባቡር ጣቢያ መገኘት ይኖርበታል፡፡
ሃምሳ ደቂቃዎች አሉት… ብዙ መቆየት የለበትም ርብቃ ጋ ቶሎ አይቷት መውጣት አለበት። መጨከን አለበት… መጨከን መጨከን፡፡.....
💫ይቀጥላል💫
ናትናኤል ከዘውዲቱ የሚለይበት ሰዓት እንደደረሰ የተገነዘበው ከአንድ ቀን በፊት ነበር፡፡ የምሥራች “እማዬ ጋ... ድሬዳዋ” ካለችው ወዲያ:: ዘወዲቱን ሊሰናበታት ደግሞ ምክንያት መስጠት አለበት፡፡ ቢሆንም ችግሩ ሁሉ እንደተፈታ አድርጎ መቅረብ የለበትም፡፡ መጪው አይታወቅም፡፡ ማን ያውቃል.. ተመልሶ ወደ አዲስ ኣበባ መምጣትና መሸሸግ ያስፈልገው ይሆናል፡፡ ያን ጊዜ የት ይገባል? ዞሮ መግቢያው መሽሽጊያው ነች ዘወዲቱ፡፡
“አዎ ተያዝ ዘውድዬ እየተመረመረ ነው አሉ፡፡ ግን ገና ነው! ያመነ አይመስለኝም፡፡
እሺ...አለች ለተጨማሪ ወሬ ጓጉታ ድዷ ውስጥ የገባ ምግብ በምላሷ እየጠረገች፡፡
ግን መጥፎ ወሬ ሰማሁ…“
“ምን?'' ቅንድቦቿን አጠበበቻቸው::
“ፖሊሶች አዲስ ኣበባ ውስጥ መደበቄን ደርሰውበታል አሉ፡፡ ያየኝ ሰው ሳይመራብኝ አልቀረም::”
ገብርኤልን.…” ደነገጠች:: “እንዴት አወቅህ? ።
“በየዘመዶቼና በየጓደኞቹ ቤት እየዞሩ ሲያጠያይቁ ነው እሉ የሰነበቱት፡፡” አላት ሃሳብ እንደገባው ሁሉ አይኖቹን ቡዝዝ አድርጎ ለምጻም ግድግዳዋ ላይ ተክሎ፡፡
“አይዞህ፡፡ እዚህ ሊያገኙህ አይችሉም፤ ከቤት ያለመውጣት ነው... ድምፅህን ካጠፋህ…” ታረጋጋው ጀመረች::
“አይ ዘውድዬ…. እኔም ተይዤ ለኣንቺም መዘዝ ከምሆን ከአዲስ አበባ ብወጣ ይሻላል:: እማዬጋ ልሄድ ነው ያሰብኩት::”
“የት ናቸው እናትህ?"- .
“ደብረብርሃን፡፡”
ከሰዓት በኋላ ጀለቢያውን ነጠላ ጫማውን ሌሎቹንም እቃዎቹን
በሸራው ቦርሳ ውስጥ ቀርቅቦ፤ በተቃወለ ጥቁር ዘይት የተጨማለቀ ቱታውን አጥልቆ፣ ልፍስፍስ ባርኔጣውን አድርጎ ተሰናበታት፡፡
“ልክ አይደለሀም፡፡ ይሄን ያህል ጊዜ አብረን ቆይተን ዘመን መለወጫ ሁለት ቀን ሲቀረው ትተኸኝ ትሄዳለህ? በፍጹም ልክ አይደለም፡፡ ምናለበት
ሁለት ቀን ቆይተህ እንቁጣጣሽን አብረን ብናሳልፍ ተለማመጠችው::
“አይሆንም ዘዉድዩ:: ከደረሱብኝ መጥፎ ነው::" አለ ጊዜ ማጥፋት እንደማይገባው ለራሱ እየመከረ፡፡ ዘውድዬ ይሄን ለአንቺ ነው የገዛሁት፡፡” አላት ሽቶውንና ነጠላ ጫማውን እየሰጣት፡፡ “ብድር መመለሴ አይደለም፤ ብድርሽን የምመልሰው ጥሩ ቀን ሲመጣ ነው፡፡ ይሄን ለዘመን መለወጫ ነው የገዛሁልሽ፡፡”
የዘውዲቱ ዓይኖች በእንባ ተሞሉ፡፡ ለስላሳነት ሲያይባት የመጀመሪያ ጊዜው ነበር፡፡ ሁሌ ተናጋሪ ሁሌ ግድ የለሽ ነበረች ዘውዲቱ፡፡አይኖቿ ውስጥ ያቆረዘዘውን እንባ ሲመለከት እሷም ለስላሳ፣ እሷም ሙቅ እንደሆነች ተረዳ፡፡
ዘላ አንገቱ ላይ ተጠመጠመችበት፡፡
ከዘውዲቱ ቤት ሲወጣ ዘጠኝ ሰዓት አልሞላም ነበር፡፡ ወደ ድሬዳዋ የሚጓዘው ባቡር ምሽት ላይ ይነሳል፡፡ ወደ ድሬዳዋ ከመሄዱ በፊት ግን ርብቃ መሥሪያ ቤት ለመደወል ወሰነ::
ርብቃ መሥሪያ ቤት ሲደውል ምህረትን ሲያገኝ ግን ያልጠበቀው ዱብ ዕዳ ጭንቅላቱን መታው የሱ ርብቃ አርግዛለች…የሱ ርብቃ ልጁን በሆዷ ተሸክማ ብቻዋን ትጨነቃለች.… የሱ ርብቃ…
ናትናኤል ወደኋላ ጋለል ካለበት ወንበር ላይ ቀና ኣለና ተቀመጠ፡፡ሰዓቱን ተመለከተ አስራ ኣንድ ተኩል ሊል ነው፡፡ የርብቃን ወንድም በአስራ ሁለት ተኩል ነው የቀጠረው፡፡ አንድ ሰዓት አለው ማለት ነው::
ከተቀመጠበት ተነስቶ ከቡና ቤቱ ወጣ፡፡ ሰማዩ ላይ ያዘበዘበው እርጉዝ ደመና ሌሊቱን ሀይለኛ ዝናብ ሊጥል እንዳሰበ ያስታውቃል፡፡ ለገሃር ታክሲ ይዞ በቸርችል ጎዳና ሽቅብ ወደ ፒያሳ ወደ ርብቃ አፓርታማ አመራ።
መጠንቀቅ አለበት፡፡ በቤቷ አካባቢ የሚያንዣብቡ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ሲገባና ሲወጣ መታየት የለበትም፡፡ አለበለዚያ እሮጦ ከእጃቸው እንደገባላቸው ነው የሚቆጠር፡፡ መጠንቀቅ አለበት፡፡ ቀጥታ ወደ ክፍሏ
ማምራት የለበትም። መሰለል… ዙሪያውን ማጥናትና መጠንቀቅ አለበለዚያ
ለሷም ተጨማሪ ችግር ነው የሚፈጥርባት፡
ርብቃ አፓርትመንት ከመድረሱ በፊት እራቅ ብሎ ከታክሲ ወረደና የስራ ሻንጣውን ትከሻው ላይ አንግቦ ጭንቅላቱ ላይ የደፋትን የጨርቅ ቆብ ወደ ታች ወደ ግንባሩ እየጎተተ በመንገዱ ቁልቁል በእርጋታ ወረደ፡፡ ሰዓቱ ገና ቢሆንም ከዳር እስከ ዳር ያንዣበበው ጥቁር ደመና አካባቢውን የመሸ አስመስሎታል፡፡ ሰዓቱን ተመለከተ፡፡ በአንድ ሰዓት አካባቢ ባቡር ጣቢያ መገኘት ይኖርበታል፡፡
ሃምሳ ደቂቃዎች አሉት… ብዙ መቆየት የለበትም ርብቃ ጋ ቶሎ አይቷት መውጣት አለበት። መጨከን አለበት… መጨከን መጨከን፡፡.....
💫ይቀጥላል💫
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ከዘጠኝ ዓመታት በፊት
ዴሪክ ዊልያምስ ሙሉ መስታወት በሆነው የቢሮ በር አሻግሮ ከእንግዳ
ማረፊያ ክፍል ውስጥ የተቀመጡትን ባል እና ሚስቶችን እየተመለከታቸው
ነው፡፡
ቢሮው ትልቅ እና ውድ በሆኑ እቃዎች የተሞላ ነው፡፡ የእንግዳ ማረፊያ ክፍሉም ቢሆን ኮርኒሱ ከፍ ብሎ የተሰራ ከመሆኑም በላይ በጥሩ የዲዛይን ባለሙያ እና በደንብ ባጌጡ ሶፋዎች የተሞላ ነው፡፡
ጠረጴዛዎቹ ላይም ላይፍ ስታይል መፅሄቶች ሞልተውታል፡፡ ይህ እንዲሆን ያደረገችው ደግሞ የዴሪክ ዊልያምስ አዲሱ ሚስቱ ሎርያን ነች፡፡
“ማሬ ገንዘብ ለማግኘት እኮ ገንዘብ ማውጣት ይኖርብናል” የሚለው
ምክርዋ ዋነኛው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ “ሰዎችን መጀመሪያ ባገኘሃቸው
ጊዜ ነው ልታስደስታቸው የምትችለው ሌላ እድል የለህም” የሚለው ነው።
ዴሪክ የሎርያንን ምክር ተግባራዊ ያደርግ የነበረው ስለምወዳት ነው ብሎ
ያስባል ወይንም ደግሞ ምርጥ ጡቶችና ያበደ መቀመጫ ስላላት እና ሌሎች
ሰዎችን ትታ እሱን በመምረጥዋ ሊሆን ይችላል ብሎ አንዳንዴ ይፈላሰፋል።
ለማንኛውም ይሄ “ገንዘብ ለማግኘት እኮ ገንዘብ ማውጣት ይኖርብናል የሚለው ፍልስፍና ሲሰራ ተመልክቷል። ምክንያቱም አዲሱ ቢሮው ከተሰራ
በኋላ የእሱ ተፈላጊነት በስልሳ ፐርሰንት ጨምሯል። ገቢውም ቢሆን በሶስት
እጥፍ ለማደግ ችሏል፡፡ ምናልባትም ይሄ
ሊሆን የቻለው ሰዎች ለሚያገኙት
አገልግሎት ብዙ ገንዘብ ሲያወጡ ነገሩ እንደሚከናወንላቸው ስለሚያምኑ ሊሆን ይችላል፡፡ ማንም ሰው ደግሞ እርካሽ የሆነ አገልግሎት አይፈልግም ብላ ሚስቱ የምትነግረው ነገር ትክክል ስለሆነም ሊሆን ይችላል፡፡
የዛሬዎቹ ጥንዶች ግን ለዴሪክ አገልግሎት የከፈሉት ክፍያ ትንሽ
ከመሆኑም በላይ ከዚህ በፊትም ለሰራላቸው የተለያዩ ምርመራዎች
ያልከፈሉት ብዙ ዕዳዎች አለባቸው፡፡ ለምን እንደሆነ አያውቀውም ብቻ
ለእነርሱ ከልብ የመነጨ የሃዘኔታ ስሜት ይሰማዋል። ለምንስ ዛሬ ሊያገኙት
እንደመጡ ሲያስብ ደግሞ ልቡን ፍርሃት ፍርሃት ብሎታል። እነሱ ግን እጅ
ለእጅ ተያይዘው እና ጣቶቻቸውን አቆላልፈው ጎን ለጎን ተቀምጠዋል።
ሰውዬው ተከር ክላንሲ ይባላል፡፡ ጥቅጥቅ ያለ በደንብ የተገነባ ሰውነት
አለው፡፡ ደንዳና አንገቱን ጥብቅ አድርጎ በሸሚዙ ስለቆለፈው የታነቀ ይመስላል፡፡ ካኪ ሱሪ እና ጂንስ ሱሪ ለብሷል፡፡ ወግ አጥባቂ ነገርም ስለሆነ ምናልባት ልብሱን ሲያወልቅ ሰውነቱ ላይ የሪፐብሊካን ፓርቲ ምልክት የሆነውን ዝሆን ተነቅሶት ሊሆን ይችላል፡፡ ሁሉ ነገሩን በጥንቃቄ እና
በስርአቱ የሚከውን ሰው መሆኑን ፊቱን በማየት ብቻ ማወቅ ይቻላል። ያም
ቢሆን ግን የደረሰበት ከፍተኛ ሀዘን እና ውስጣዊ ሀዘኑን ከፊቱ ላይ ማንበብ
ይቻላል። ዕድሜው በአርባዎቹ አጋማሽ ላይ ቢገኝም ሲታይ ግን የስልሳ
አመት ሽማግሌ ነበር የሚመስለው፡፡ አንድ ልጅን በሞት ማጣትን የሚመስል
ከባድ ሀዘን አይገኝም፡፡ ነገር ግን ይህቺን አንድ ልጅህን ጠፍታ ሳትገኝ መቅረትዋ በወላጅ የዋህ ልብም የጠፋችው ልጅ የሆነ ቀን ላይ ተገኝታ ወደ ቤትዋ በመመለስ የወላጆችዋን ስቃይ እንዲያበቃ ታደርጋለች ብሎ መጠበቅን
የመሰለ እጅግ በጣም ስሜትን የሚጎዳ ነገር እንደሌለ ዴሪክ ዊልያምስ በደንብ
ይገባዋል፡፡
ባለቤቱ ሜሪ ግን በጥሩ ሁኔታ ላይ የምትገኝ ትመስላለች። እርግጥ ነው
እሷም ብትሆን ይደክማታል፤ ያም ሆኖ ግን የልጅዋን ዕጣ ፈንታ ከባሏ በታቃራኒ መልኩ ተቀብላ ነገረ አለሙን ሁሉ ረስታ የተቀመጠች ሴት ሆናለች፡፡ ለዚህም ሊሆን ይችላል በውስጧ የሚገኘውን ስቃይዋን ፊቷ ላይ ማንበብ የማይቻለው፡፡ ይሄ ጥሩ ነው፤ ቢያንስ ከሁለቱ አንዱ እውነታውን ተቀብለውታል ብሎ ዊልያምስ አሰበ፡፡
ለሶስት ሳምንት ያህል ሜክሲኮ ሲቲ ውስጥ ዊሊያምስ የክላንሲን ልጅ
ቻርሎቴን ለመፈለግ ሲኳትን ነበር፡፡
ከመጥፋትዋ በፊት ያሉትን የቻርሎቴ
ውሎዎችን አና ያገኘቻቸውን ሰዎች በማግኘትም ዱካዋን ለመፈለግ ጥረት
ሲያደርግ ቆየ፡፡ ቆንጅየዋ ቻርሎቴ ክላንሲ ረጅም ናት፤ በተለይ ደግሞ ከሃገሬው የሜክሲኮ ሴቶች አንጻር በቀላሉ በምትኖርበት አካባቢ የምትለይ
ቢሆንም ከጠፋችበት ምሽት በኋላ ማንም ሰው አይቷት እንደማያውቅ ነበር
የነገሩት፡፡
በመጀመሪያ ጊዜ ባል እና ሚስቱ የቻርሎቴ ወላጆች ስለ ቻርሎቴ የፍለጋ
ሁኔታ በደንብ አልነገሩትም ነበር፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት አባቷ ተከር አላንሲ የውጭ ሀገር ፖሊሶች በተለይ ደግሞ የሜክሲኮ ፖሊሶች በሙሉ የማይረቡ ናቸው ብሎ ስለሚያምን ነበር፡፡ ስለዚህም በፍለጋው ላይ ምናልባትም ኤፍ.ቢ.አይ እና በሜክሲኮ የአሜሪካ ቆንስላ በጉዳዩ ላይ ቢገቡበት ልጁ የምትገኝ መስሎት ነበር፡፡ ነገር ግን በሚገርም ሁኔታ ከሜክሲኮ ፖሊሶች በባሰ መልኩ የልጁን ጉዳይ ችላ ስላሉት ንዴቱን በዚህ
መልኩ ነበር የገለጸለት፡፡
“ስለ ቻርሊ እኮ ምንም ደንታ የላቸውም” ብሎ በመጮህ ነበር ተከር ክላንሲ በሁሉም ነገር ተስፋ ቆርጦ እሱን ለመቅጠር በመጣ ጊዜ የተናገረው
እሷ የአሜሪካ ዜግነት ያላት ሴት አይደለችም እንዴ? ታዲያ ለምንድነው
በየጥሻው ውስጥ የማይፈልጓት?”
ዊልያምስ የተከር ክላንሲ ንዴት ይገባዋል ግን ደግሞ በኤፍ.ቢ.አይ እና በቆንጽላው ጽ/ቤት አልተገረመም፡፡ “አሳዛኙ ነገር ግን ምን መሰላችሁ ቻርሎቴን በደንብ ሊፈልጓት የሚችሉት እሷ የሀብታም ልጅ ወይንም የባለስልጣን ልጅ ብትሆን ነበር፡፡ ስለሆነም የኤፍ ቢ አይ ሰዎች እሷን ለመፈለግ ጊዜያቸውን እና ሀብታቸውን ማውጣት አይፈልጉም፡፡ እሷ
ለመጨረሻ ጊዜ ወደ እናንተ ስትደውልላችሁ እድሜዋ ከ18 አመት በላይ ነበር፡፡ ብዙ ልጆች ደግሞ በዚህ እድሜያቸው ላይ ለወላጆቻቸው ሳይናገሩ
ከሆነ ሰው ጋር ሊጠፉ ይችላሉ፡፡”
ቻርሊ በፍፁም እንደዚህ ያለ ነገር አታደርግም” አለ ተከር ክላንሲ፡፡በዚያ ላይ ደግሞ ለአመታት ያህል በእኛ ላይ ጨክና ሳታናግረን አትተወንም፡፡” ሲል ሚስቱም ቀጠል አድርጋ “ሚስተር ዊልያምስ የሆነ ነገር ልጃችን ላይ እንደደረሰባት ይታወቀናል” ብላ እምባዋን ታግላ አስቀረችው እና ወይዘሮ ባደን እንደነገረችንኸውን ሜክሲኮ ውስጥ በየአመቱ ቱሪስቶች እና ሌሎች ሰዎች እንደሚታገቱ ነው፡፡”
“ምን አልሽኝ?” ብሎ ዊልያምስ ጠየቀ፡፡
“ቫለንቲና ባደን ናት፡፡ የዊሊ ባደን ሚስት ናት፡፡ የጠፉ ሰዎችን የሚያፈላልጉ የበጎ አድራጎት ድርጅት የከፈተች ናት።ከማንም በላይ ቻርሎቴን ለመፈለግ እገዛ አድርጋልናለች አለው ተከር ክላንሲ፡፡”
ይህንን ሲሰማ በድንገት አንድ ነገር ትዝ አለው ተከር፡፡ የሆነ ማታ ላይ ሁለት ታላላቅ ክለቦች እየተጫወቱ በነበሩበት የእራት ሰዓት ላይ ልጆቻቸውን እንዲያፈላልጉላቸው ሲማጸኑ እንደነበር አስታወሰ፡፡ ያኔ በዚህ የእረፍት ሰዓት ላይ ለሚተላለፉ ማንኛውም ነገሮች በጣም ውድ የሆነ ዋጋ ለቲቪ ጣቢያዎች ተከፍሎ ነው፡፡ ስለዚህም ይህንን የማስታውቂያ ክፍያ የከፈለችው
የዊሊ ባደን ሚስት ቫለንቲና ባደን መሆንዋን ተረዳ፡፡
“በፍፁም ወደዚያ እንድትሄድ ልፈቅድላት አይገባኝም ነበር፡፡” አለ ተከር ክላንሲ በቁጭት፡፡
“ምን መሰለህ ሚስ ባደን በእገታ የተወሰዱ ሰዎችን በማፈላለግና
ለአጋቾቹ የማስለቀቂያ ክፍያ እየከፈለች ታጋቾችን ከቤተሰቦቻቸው ጋር
እንደምታገኛኝ ነው የምናውቀው፡፡ ይሄው እንግዲህ ስለልጃችን ግን አንድም
ሰው እስካሁን ድረስ የደወለልን የለም፡፡ ይሄ ነገር ጥሩ ይሁን መጥፎ ሊገባን
አልቻለም” አለችው ሜሪ ክላንሲ፡፡
መጥፎ ነው እንጂ ብሎ አሰበ ዊልያምስ ደግሞም ይህቺ ቫለንቲና
ባደን ለቻርሎቴ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ስምንት
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
....ከዘጠኝ ዓመታት በፊት
ዴሪክ ዊልያምስ ሙሉ መስታወት በሆነው የቢሮ በር አሻግሮ ከእንግዳ
ማረፊያ ክፍል ውስጥ የተቀመጡትን ባል እና ሚስቶችን እየተመለከታቸው
ነው፡፡
ቢሮው ትልቅ እና ውድ በሆኑ እቃዎች የተሞላ ነው፡፡ የእንግዳ ማረፊያ ክፍሉም ቢሆን ኮርኒሱ ከፍ ብሎ የተሰራ ከመሆኑም በላይ በጥሩ የዲዛይን ባለሙያ እና በደንብ ባጌጡ ሶፋዎች የተሞላ ነው፡፡
ጠረጴዛዎቹ ላይም ላይፍ ስታይል መፅሄቶች ሞልተውታል፡፡ ይህ እንዲሆን ያደረገችው ደግሞ የዴሪክ ዊልያምስ አዲሱ ሚስቱ ሎርያን ነች፡፡
“ማሬ ገንዘብ ለማግኘት እኮ ገንዘብ ማውጣት ይኖርብናል” የሚለው
ምክርዋ ዋነኛው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ “ሰዎችን መጀመሪያ ባገኘሃቸው
ጊዜ ነው ልታስደስታቸው የምትችለው ሌላ እድል የለህም” የሚለው ነው።
ዴሪክ የሎርያንን ምክር ተግባራዊ ያደርግ የነበረው ስለምወዳት ነው ብሎ
ያስባል ወይንም ደግሞ ምርጥ ጡቶችና ያበደ መቀመጫ ስላላት እና ሌሎች
ሰዎችን ትታ እሱን በመምረጥዋ ሊሆን ይችላል ብሎ አንዳንዴ ይፈላሰፋል።
ለማንኛውም ይሄ “ገንዘብ ለማግኘት እኮ ገንዘብ ማውጣት ይኖርብናል የሚለው ፍልስፍና ሲሰራ ተመልክቷል። ምክንያቱም አዲሱ ቢሮው ከተሰራ
በኋላ የእሱ ተፈላጊነት በስልሳ ፐርሰንት ጨምሯል። ገቢውም ቢሆን በሶስት
እጥፍ ለማደግ ችሏል፡፡ ምናልባትም ይሄ
ሊሆን የቻለው ሰዎች ለሚያገኙት
አገልግሎት ብዙ ገንዘብ ሲያወጡ ነገሩ እንደሚከናወንላቸው ስለሚያምኑ ሊሆን ይችላል፡፡ ማንም ሰው ደግሞ እርካሽ የሆነ አገልግሎት አይፈልግም ብላ ሚስቱ የምትነግረው ነገር ትክክል ስለሆነም ሊሆን ይችላል፡፡
የዛሬዎቹ ጥንዶች ግን ለዴሪክ አገልግሎት የከፈሉት ክፍያ ትንሽ
ከመሆኑም በላይ ከዚህ በፊትም ለሰራላቸው የተለያዩ ምርመራዎች
ያልከፈሉት ብዙ ዕዳዎች አለባቸው፡፡ ለምን እንደሆነ አያውቀውም ብቻ
ለእነርሱ ከልብ የመነጨ የሃዘኔታ ስሜት ይሰማዋል። ለምንስ ዛሬ ሊያገኙት
እንደመጡ ሲያስብ ደግሞ ልቡን ፍርሃት ፍርሃት ብሎታል። እነሱ ግን እጅ
ለእጅ ተያይዘው እና ጣቶቻቸውን አቆላልፈው ጎን ለጎን ተቀምጠዋል።
ሰውዬው ተከር ክላንሲ ይባላል፡፡ ጥቅጥቅ ያለ በደንብ የተገነባ ሰውነት
አለው፡፡ ደንዳና አንገቱን ጥብቅ አድርጎ በሸሚዙ ስለቆለፈው የታነቀ ይመስላል፡፡ ካኪ ሱሪ እና ጂንስ ሱሪ ለብሷል፡፡ ወግ አጥባቂ ነገርም ስለሆነ ምናልባት ልብሱን ሲያወልቅ ሰውነቱ ላይ የሪፐብሊካን ፓርቲ ምልክት የሆነውን ዝሆን ተነቅሶት ሊሆን ይችላል፡፡ ሁሉ ነገሩን በጥንቃቄ እና
በስርአቱ የሚከውን ሰው መሆኑን ፊቱን በማየት ብቻ ማወቅ ይቻላል። ያም
ቢሆን ግን የደረሰበት ከፍተኛ ሀዘን እና ውስጣዊ ሀዘኑን ከፊቱ ላይ ማንበብ
ይቻላል። ዕድሜው በአርባዎቹ አጋማሽ ላይ ቢገኝም ሲታይ ግን የስልሳ
አመት ሽማግሌ ነበር የሚመስለው፡፡ አንድ ልጅን በሞት ማጣትን የሚመስል
ከባድ ሀዘን አይገኝም፡፡ ነገር ግን ይህቺን አንድ ልጅህን ጠፍታ ሳትገኝ መቅረትዋ በወላጅ የዋህ ልብም የጠፋችው ልጅ የሆነ ቀን ላይ ተገኝታ ወደ ቤትዋ በመመለስ የወላጆችዋን ስቃይ እንዲያበቃ ታደርጋለች ብሎ መጠበቅን
የመሰለ እጅግ በጣም ስሜትን የሚጎዳ ነገር እንደሌለ ዴሪክ ዊልያምስ በደንብ
ይገባዋል፡፡
ባለቤቱ ሜሪ ግን በጥሩ ሁኔታ ላይ የምትገኝ ትመስላለች። እርግጥ ነው
እሷም ብትሆን ይደክማታል፤ ያም ሆኖ ግን የልጅዋን ዕጣ ፈንታ ከባሏ በታቃራኒ መልኩ ተቀብላ ነገረ አለሙን ሁሉ ረስታ የተቀመጠች ሴት ሆናለች፡፡ ለዚህም ሊሆን ይችላል በውስጧ የሚገኘውን ስቃይዋን ፊቷ ላይ ማንበብ የማይቻለው፡፡ ይሄ ጥሩ ነው፤ ቢያንስ ከሁለቱ አንዱ እውነታውን ተቀብለውታል ብሎ ዊልያምስ አሰበ፡፡
ለሶስት ሳምንት ያህል ሜክሲኮ ሲቲ ውስጥ ዊሊያምስ የክላንሲን ልጅ
ቻርሎቴን ለመፈለግ ሲኳትን ነበር፡፡
ከመጥፋትዋ በፊት ያሉትን የቻርሎቴ
ውሎዎችን አና ያገኘቻቸውን ሰዎች በማግኘትም ዱካዋን ለመፈለግ ጥረት
ሲያደርግ ቆየ፡፡ ቆንጅየዋ ቻርሎቴ ክላንሲ ረጅም ናት፤ በተለይ ደግሞ ከሃገሬው የሜክሲኮ ሴቶች አንጻር በቀላሉ በምትኖርበት አካባቢ የምትለይ
ቢሆንም ከጠፋችበት ምሽት በኋላ ማንም ሰው አይቷት እንደማያውቅ ነበር
የነገሩት፡፡
በመጀመሪያ ጊዜ ባል እና ሚስቱ የቻርሎቴ ወላጆች ስለ ቻርሎቴ የፍለጋ
ሁኔታ በደንብ አልነገሩትም ነበር፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት አባቷ ተከር አላንሲ የውጭ ሀገር ፖሊሶች በተለይ ደግሞ የሜክሲኮ ፖሊሶች በሙሉ የማይረቡ ናቸው ብሎ ስለሚያምን ነበር፡፡ ስለዚህም በፍለጋው ላይ ምናልባትም ኤፍ.ቢ.አይ እና በሜክሲኮ የአሜሪካ ቆንስላ በጉዳዩ ላይ ቢገቡበት ልጁ የምትገኝ መስሎት ነበር፡፡ ነገር ግን በሚገርም ሁኔታ ከሜክሲኮ ፖሊሶች በባሰ መልኩ የልጁን ጉዳይ ችላ ስላሉት ንዴቱን በዚህ
መልኩ ነበር የገለጸለት፡፡
“ስለ ቻርሊ እኮ ምንም ደንታ የላቸውም” ብሎ በመጮህ ነበር ተከር ክላንሲ በሁሉም ነገር ተስፋ ቆርጦ እሱን ለመቅጠር በመጣ ጊዜ የተናገረው
እሷ የአሜሪካ ዜግነት ያላት ሴት አይደለችም እንዴ? ታዲያ ለምንድነው
በየጥሻው ውስጥ የማይፈልጓት?”
ዊልያምስ የተከር ክላንሲ ንዴት ይገባዋል ግን ደግሞ በኤፍ.ቢ.አይ እና በቆንጽላው ጽ/ቤት አልተገረመም፡፡ “አሳዛኙ ነገር ግን ምን መሰላችሁ ቻርሎቴን በደንብ ሊፈልጓት የሚችሉት እሷ የሀብታም ልጅ ወይንም የባለስልጣን ልጅ ብትሆን ነበር፡፡ ስለሆነም የኤፍ ቢ አይ ሰዎች እሷን ለመፈለግ ጊዜያቸውን እና ሀብታቸውን ማውጣት አይፈልጉም፡፡ እሷ
ለመጨረሻ ጊዜ ወደ እናንተ ስትደውልላችሁ እድሜዋ ከ18 አመት በላይ ነበር፡፡ ብዙ ልጆች ደግሞ በዚህ እድሜያቸው ላይ ለወላጆቻቸው ሳይናገሩ
ከሆነ ሰው ጋር ሊጠፉ ይችላሉ፡፡”
ቻርሊ በፍፁም እንደዚህ ያለ ነገር አታደርግም” አለ ተከር ክላንሲ፡፡በዚያ ላይ ደግሞ ለአመታት ያህል በእኛ ላይ ጨክና ሳታናግረን አትተወንም፡፡” ሲል ሚስቱም ቀጠል አድርጋ “ሚስተር ዊልያምስ የሆነ ነገር ልጃችን ላይ እንደደረሰባት ይታወቀናል” ብላ እምባዋን ታግላ አስቀረችው እና ወይዘሮ ባደን እንደነገረችንኸውን ሜክሲኮ ውስጥ በየአመቱ ቱሪስቶች እና ሌሎች ሰዎች እንደሚታገቱ ነው፡፡”
“ምን አልሽኝ?” ብሎ ዊልያምስ ጠየቀ፡፡
“ቫለንቲና ባደን ናት፡፡ የዊሊ ባደን ሚስት ናት፡፡ የጠፉ ሰዎችን የሚያፈላልጉ የበጎ አድራጎት ድርጅት የከፈተች ናት።ከማንም በላይ ቻርሎቴን ለመፈለግ እገዛ አድርጋልናለች አለው ተከር ክላንሲ፡፡”
ይህንን ሲሰማ በድንገት አንድ ነገር ትዝ አለው ተከር፡፡ የሆነ ማታ ላይ ሁለት ታላላቅ ክለቦች እየተጫወቱ በነበሩበት የእራት ሰዓት ላይ ልጆቻቸውን እንዲያፈላልጉላቸው ሲማጸኑ እንደነበር አስታወሰ፡፡ ያኔ በዚህ የእረፍት ሰዓት ላይ ለሚተላለፉ ማንኛውም ነገሮች በጣም ውድ የሆነ ዋጋ ለቲቪ ጣቢያዎች ተከፍሎ ነው፡፡ ስለዚህም ይህንን የማስታውቂያ ክፍያ የከፈለችው
የዊሊ ባደን ሚስት ቫለንቲና ባደን መሆንዋን ተረዳ፡፡
“በፍፁም ወደዚያ እንድትሄድ ልፈቅድላት አይገባኝም ነበር፡፡” አለ ተከር ክላንሲ በቁጭት፡፡
“ምን መሰለህ ሚስ ባደን በእገታ የተወሰዱ ሰዎችን በማፈላለግና
ለአጋቾቹ የማስለቀቂያ ክፍያ እየከፈለች ታጋቾችን ከቤተሰቦቻቸው ጋር
እንደምታገኛኝ ነው የምናውቀው፡፡ ይሄው እንግዲህ ስለልጃችን ግን አንድም
ሰው እስካሁን ድረስ የደወለልን የለም፡፡ ይሄ ነገር ጥሩ ይሁን መጥፎ ሊገባን
አልቻለም” አለችው ሜሪ ክላንሲ፡፡
መጥፎ ነው እንጂ ብሎ አሰበ ዊልያምስ ደግሞም ይህቺ ቫለንቲና
ባደን ለቻርሎቴ
👍2🔥1
ወላጆች ቻርሎቴን በህይወት የማግኘታቸው እድል ከመቶ
አንድ እንደሆነ ነግራታለች። ከአሜሪካ በደቡብ አዋሳኝ ላይ ያለውን የኑሮ
ሁኔታ መካከለኛ ገቢ ያላቸው የአሜሪካ ወላጆች አይረዱትም፡፡ በዚያ ላይ
ደግሞ ቻርሎቴ ወጣት እና በቀላሉ ሰው አይን ውስጥ የምትገባ ልጅ ስለነበረች እሷን በህይወት ዳግመኛ ማየት በጣም ጠባብ ነው፡፡
ለማንኛውም የቻርሎቴ ወላጆች ዴሪክ ዊልያምስ ቻርሎቴን እንዲፈልግ ቀጠሩት፡፡ እሱም ደግሞ በጣም በምርጥ ሁኔታ እና ያለውን አቅምም እስከመጨረሻው በመጠቀም ቻርሎቴን የመፈለግ ስራውን አከናውኖ ነበር፡፡
ዊሊያምስ የቻርሎቴ ወላጆች ከቀጠሩት ከአራት ቀናት በኋላ ሜክሲኮ
ሲቲ የገባው ቻርሎቴን ቀጥረው የሚያሰሯት ሰዎች የመኖሪያ አድራሻን እና
ቻርሎቴ ወደ ቤተሰቦችዋ ስትደውል አንድ ጊዜ የምታነሳላቸውን የጓደኛዋን የመጀመሪያ ስም ብቻ ይዞ እና ደግሞም አንዳንድ ፎቶዎችን እና ሜክሲኮ ውስጥ ስትጠቀምበት የነበረውን የስልክ ቁጥሯን ብቻ ነበር፡፡ በነገሩ ላይ ትንሽ ተስፋ እንዳለው እያወቀ ወደ ሜክሲኮ ሊመጣ የቻለበት ሌላኛው ምክንያት ደግሞ ሚስቱ ሎርያን አስር ሺህ ዶላር እኮ ቀልድ አይደለም ስላለችው ነበር እዚህ ጉዳይ ውስጥ የገባው፡፡
ሜክሲኮን ዊልያምስ ያገኛት ከጠበቀው በላይ ህግ የማይከበርበት ቦታ ሆና ነበር። በቃ ሜክሲኮ ሲቲ ማለት በህገ አራዊት የምትመራ የምእራቡ ዓለም ክፍል ሆና ነበር፡፡ ከተማውን ካየ በኋላ የቻርሎቴ ቤተሰቦች ልጃቸውን አምነው ወደዚች ከተማ መላካቸው በጤናቸው እንዳልሆነ ድምዳሜ ላይ ሊደርስ ቻለ። በየቀኑ በከተማ ውስጥ የሚደረጉት ወንጀሎች የከፉ ናቸው።የአደንዛዥ እጽ አዘዋዋሪዎች እና አጋች ሽፍቶችም በጠራራ እገታዎቻቸውን እና የእፅ ንግዳቸውን የሚያደርጉባት ከተማ ናት፡፡ እነዚህን ለመጠበቅ በጀግንነት የፖሊስነት ስራቸውን የሚሰሩ ሰዎች በተቃራኒ
የወንጀል ድርጊቶችን ጠንክረው የሚዋጉ እና የህብረተሰቡን ደህንነት ሀይሎች ቤተሰቦቻቸው እና ዘመድ አዝማዶቻቸው ላይ ሳይቀር ስቃይ ይደርስባቸዋል፡፡ በእነዚህ የወንጀል ቡድኖች ተቀጥረው የሚሰሩ ፖሊሶች ደግሞ ህብረተሰቡን ሣይሆን የእነዚህን ወንጀለኞችን ቤተሰብ የሚጠብቁ ናቸው። ብቻ የሀገሪቷ ባላስልጣኖችም ቢሆኑ ከላይ እስከታች በሙስና የተጨማለቁ ናቸው።
ቻርሎቴን ቀጥረው ሲያሰሯት የነበሩት የኢንክሪቶ ቤተሰቦች ለዘመናት ያህል በዚህ ከተማ ውስጥ ሲኖሩ የነበሩ ሲሆን ምንም የሀዘኔታ ምልክት በማይታይበት ድምጽ “እንደዚህ ያሉ ነገሮች እዚህ ከተማ ውስጥ ሲፈፀሙ ደግሞ አዲስ አይደለም፡፡ ማን ሊገድላት እንዲሚችል ትገምታለህ፡፡ ፀረ አሜሪካዊ አቋም ባላቸው ሰዎች ወይንስ ቤተሰቦችዋ ሀብታሞች ናቸው ብለው በገመቱና የእገታ ማስለቀቂያ ገንዘብን ለመጠየቅ ባሰቡ ሰዎች ግን ያው እንደምታውቀው እስከ አሁን ድረስ ምንም አይነት ጥያቄ ከቤተሰቦችዋ አልመጣም፡፡” አሉት፡፡
ይሄኔ ጥቁር ፀጉር ያላት ቆንጅዬ የጁሃን ሚስት የሆነችው አንጀሊና ኢንክሪቶ ጣልቃ ገባችና “ሚስተር ዊልያምስ በእኛ ከተማ ውስጥ የወሮበላ ቡድኖች ያለምንም ምክንያት ነው አንድን ሰው እንደፈለጉ የሚያደርጉት።ለዚህም ብለን ነበር ቻርሊን ብቻዋን መኪና እንዳታሽከረክር አስጠንቅቀናት
የነበረው፡፡ ይህም ሆኖ ግን እሷ ልትስማን ፈቃደኛ አልነበረችም።”
“እና እሷ ይህን ስታደርግ ልታስቆሟት አልሞከራችሁም ነበር? ማታስ ላይ የእናንተን መኪና ይዛ ስትወጣ አይሆንም ለምንድን ነው ያላላችኋት?” ብሎ ዊልያምስ በንዴት ተሞልቶ ጠየቃቸው፡፡
“እኛ እኮ ቻርሎትን የቀጠርናት ልጃችንን እንድትቆጣጠር ብለን ነው” ብሎ ጁሃን ሞገተ፡፡ እና በመቀጠልም “ስለዚህ እሷ በግል ጊዜዋ የምታደርጋቸውን ነገሮች አድርጊ ወይም አታድርጊ እያልን ልንቆጣጠራት አንችልም፡፡”
በዚያ ላይ ደግሞ ቆንጆ እንደመሆኗ መጠን ምናልባትም እኛን የማትሰማበት ከሰዎች ጋር የወሲብ ግንኙነት ይኖራትም ይሆናል፡፡” አለችው አንጀሊና፡፡
“እናንተ የምታውቁት የወንድ ጓደኛ ነበራት?” ብሎ ሲጠይቃቸው ሁለቱም በአሉታ ራሳቸውን ወዝውዘው አናውቅም ብለው መለሱ፡፡......
✨ይቀጥላል✨
አንድ እንደሆነ ነግራታለች። ከአሜሪካ በደቡብ አዋሳኝ ላይ ያለውን የኑሮ
ሁኔታ መካከለኛ ገቢ ያላቸው የአሜሪካ ወላጆች አይረዱትም፡፡ በዚያ ላይ
ደግሞ ቻርሎቴ ወጣት እና በቀላሉ ሰው አይን ውስጥ የምትገባ ልጅ ስለነበረች እሷን በህይወት ዳግመኛ ማየት በጣም ጠባብ ነው፡፡
ለማንኛውም የቻርሎቴ ወላጆች ዴሪክ ዊልያምስ ቻርሎቴን እንዲፈልግ ቀጠሩት፡፡ እሱም ደግሞ በጣም በምርጥ ሁኔታ እና ያለውን አቅምም እስከመጨረሻው በመጠቀም ቻርሎቴን የመፈለግ ስራውን አከናውኖ ነበር፡፡
ዊሊያምስ የቻርሎቴ ወላጆች ከቀጠሩት ከአራት ቀናት በኋላ ሜክሲኮ
ሲቲ የገባው ቻርሎቴን ቀጥረው የሚያሰሯት ሰዎች የመኖሪያ አድራሻን እና
ቻርሎቴ ወደ ቤተሰቦችዋ ስትደውል አንድ ጊዜ የምታነሳላቸውን የጓደኛዋን የመጀመሪያ ስም ብቻ ይዞ እና ደግሞም አንዳንድ ፎቶዎችን እና ሜክሲኮ ውስጥ ስትጠቀምበት የነበረውን የስልክ ቁጥሯን ብቻ ነበር፡፡ በነገሩ ላይ ትንሽ ተስፋ እንዳለው እያወቀ ወደ ሜክሲኮ ሊመጣ የቻለበት ሌላኛው ምክንያት ደግሞ ሚስቱ ሎርያን አስር ሺህ ዶላር እኮ ቀልድ አይደለም ስላለችው ነበር እዚህ ጉዳይ ውስጥ የገባው፡፡
ሜክሲኮን ዊልያምስ ያገኛት ከጠበቀው በላይ ህግ የማይከበርበት ቦታ ሆና ነበር። በቃ ሜክሲኮ ሲቲ ማለት በህገ አራዊት የምትመራ የምእራቡ ዓለም ክፍል ሆና ነበር፡፡ ከተማውን ካየ በኋላ የቻርሎቴ ቤተሰቦች ልጃቸውን አምነው ወደዚች ከተማ መላካቸው በጤናቸው እንዳልሆነ ድምዳሜ ላይ ሊደርስ ቻለ። በየቀኑ በከተማ ውስጥ የሚደረጉት ወንጀሎች የከፉ ናቸው።የአደንዛዥ እጽ አዘዋዋሪዎች እና አጋች ሽፍቶችም በጠራራ እገታዎቻቸውን እና የእፅ ንግዳቸውን የሚያደርጉባት ከተማ ናት፡፡ እነዚህን ለመጠበቅ በጀግንነት የፖሊስነት ስራቸውን የሚሰሩ ሰዎች በተቃራኒ
የወንጀል ድርጊቶችን ጠንክረው የሚዋጉ እና የህብረተሰቡን ደህንነት ሀይሎች ቤተሰቦቻቸው እና ዘመድ አዝማዶቻቸው ላይ ሳይቀር ስቃይ ይደርስባቸዋል፡፡ በእነዚህ የወንጀል ቡድኖች ተቀጥረው የሚሰሩ ፖሊሶች ደግሞ ህብረተሰቡን ሣይሆን የእነዚህን ወንጀለኞችን ቤተሰብ የሚጠብቁ ናቸው። ብቻ የሀገሪቷ ባላስልጣኖችም ቢሆኑ ከላይ እስከታች በሙስና የተጨማለቁ ናቸው።
ቻርሎቴን ቀጥረው ሲያሰሯት የነበሩት የኢንክሪቶ ቤተሰቦች ለዘመናት ያህል በዚህ ከተማ ውስጥ ሲኖሩ የነበሩ ሲሆን ምንም የሀዘኔታ ምልክት በማይታይበት ድምጽ “እንደዚህ ያሉ ነገሮች እዚህ ከተማ ውስጥ ሲፈፀሙ ደግሞ አዲስ አይደለም፡፡ ማን ሊገድላት እንዲሚችል ትገምታለህ፡፡ ፀረ አሜሪካዊ አቋም ባላቸው ሰዎች ወይንስ ቤተሰቦችዋ ሀብታሞች ናቸው ብለው በገመቱና የእገታ ማስለቀቂያ ገንዘብን ለመጠየቅ ባሰቡ ሰዎች ግን ያው እንደምታውቀው እስከ አሁን ድረስ ምንም አይነት ጥያቄ ከቤተሰቦችዋ አልመጣም፡፡” አሉት፡፡
ይሄኔ ጥቁር ፀጉር ያላት ቆንጅዬ የጁሃን ሚስት የሆነችው አንጀሊና ኢንክሪቶ ጣልቃ ገባችና “ሚስተር ዊልያምስ በእኛ ከተማ ውስጥ የወሮበላ ቡድኖች ያለምንም ምክንያት ነው አንድን ሰው እንደፈለጉ የሚያደርጉት።ለዚህም ብለን ነበር ቻርሊን ብቻዋን መኪና እንዳታሽከረክር አስጠንቅቀናት
የነበረው፡፡ ይህም ሆኖ ግን እሷ ልትስማን ፈቃደኛ አልነበረችም።”
“እና እሷ ይህን ስታደርግ ልታስቆሟት አልሞከራችሁም ነበር? ማታስ ላይ የእናንተን መኪና ይዛ ስትወጣ አይሆንም ለምንድን ነው ያላላችኋት?” ብሎ ዊልያምስ በንዴት ተሞልቶ ጠየቃቸው፡፡
“እኛ እኮ ቻርሎትን የቀጠርናት ልጃችንን እንድትቆጣጠር ብለን ነው” ብሎ ጁሃን ሞገተ፡፡ እና በመቀጠልም “ስለዚህ እሷ በግል ጊዜዋ የምታደርጋቸውን ነገሮች አድርጊ ወይም አታድርጊ እያልን ልንቆጣጠራት አንችልም፡፡”
በዚያ ላይ ደግሞ ቆንጆ እንደመሆኗ መጠን ምናልባትም እኛን የማትሰማበት ከሰዎች ጋር የወሲብ ግንኙነት ይኖራትም ይሆናል፡፡” አለችው አንጀሊና፡፡
“እናንተ የምታውቁት የወንድ ጓደኛ ነበራት?” ብሎ ሲጠይቃቸው ሁለቱም በአሉታ ራሳቸውን ወዝውዘው አናውቅም ብለው መለሱ፡፡......
✨ይቀጥላል✨
👍1