አትሮኖስ
286K subscribers
121 photos
3 videos
41 files
572 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
አስደግፎ ወደ እሷ አንገቱን
አስግጎ በንዴት እያያት ነው።

“እኔ ልጁ የት እንደሚገኝ አላውቅም” ብላ ኒኪ የንዴት ድምፅ ባለው ድምፀት “እንዴ እሱ የሰጠኝን የስልክ ቁጥር ሰጠኋችሁ አይደል?”

“እኮ የማይሰራ የስልክ ቁጥር?”

“ይሄውልህ እሱ እዚህ ድረስ መጥቶ ለእኔ ምስክር መሆን አይገባውም።”ብላ በንዴት መናገር ጀመረች ኒኪ በመቀጠልም “እሱ በጊዜው እዚያው
ነበር፡፡ ስለሆነም ጥቁሩ ላንድክሩዘር እኔን ሊገጭ ወደ እኔ እየገሰገሰ ሲመጣ
እዚያው ከመኖሩም በላይ ህይወቴንም በድንገት ሊያተርፍልኝ ችሏል።
አለችው፡፡

ንዴቷን ሲመለከት የነበረው ሉው ጉድማንም አኳኋኗን አይቶ እያደነቃት “ይህቺ ሴት ንዴት ይስማማታል ማለት ነው?” አለ በውስጡ።ልክ ሊናደፍ እንደተዘጋጀ ኮብራ ነበር የሆነችው። በእርግጥም ደግሞ ሚክ ጆንስን መነደፍም ይገባዋል። ምክንያቱም ትላንትና የደረሰባትን በመኪና
የሆነ ሰው ሊገድላት መሞከሩን ለእነርሱ ካመለከተች በኋላ መርማሪዎች ተረጋግተው እና ምንም አይነት የተዛባ አመለካከትን ለእሷ ሳያሳዩ ሊያናግሯት (ሊመረምሯት) ተነጋግረው ነበር። ይሄው አሁን ሚክ ጆንስን ቃሉን አፍርሶ እሷን በጣም በሚያዋርድ መልኩ እየሞገታት ይገኛል።በተለይ ደግሞ ፖሊስ በቦታው ሄዶ የፎሬንሲክ ምርመራ ሊያደርግ የሁለት መኪና ጎማዎች የመንሸራተት ምልክት (አንዱም የእሷ መርሴዲስ መኪናዋ ጎማ አይደለም) እና ከጎረቤቷ አጥር ላይም የቀይ መኪና ቀለም ፍቅፋቂ
ተገኝቶ ነበር። ስለዚህም ባልደረባው በዚህ መልኩ ለምን ድርቅ ብሎ ኒኪን
እንደሚሞግታት ሊገባው አልቻለም። ለምንስ የኒኪን ወንጀለኛነት አምኖ
በዚህ መልኩ እንደሚያናግራት ግልፅ ሊሆንለት አልቻለም።
አጠገቧ በጣም ብልግናውን በሚያሳይ መልኩ በሀይል ድምፅ አውጥቶ አዛጋ እና “እና የተሳሳተ ቁጥር ነው የሰጠሽ እና ስሙን አልጠየቅሽውም?
ወይንም ደግሞ የታርጋ ቁጥሩን አልያዝሽም?” አላት ጆንሰን፡፡

“በጣም ደንግጬ ነበር” ብላ በንዴት እየተናገረችም “የሆነ ሰው በመኪና
ገጭቶ ሊገድለኝ ሞክሮ ነበር እናም ደግሞ ይሄ ሰው ለጥቂት ነበር የሳተኝ”
ብላ አይኗን የደከመው ህፃን ልጅ ይመስል አንዴ ካሸችው በኋላም “ታካሚዬ ተገድላለች፤ ረዳቴም ተገድሏል፡፡ ሌሎችም በሽተኞቼ እንገደላለን ብለው በጣም በፍርሃት ውስጥ ይገኛሉ። ከእነዚህ ግድያዎች ጀርባ እኔን የሚፈልግ ሰው አለ ብለህ የነገርከኝ አንተው ነህ፡፡ አሁን ልክ የሆንክ ይመስለኛል ምክንያቱም እኔንም ይሄ ሰው ሊገድለኝ ሞክሮ አልተሳካለትም። ስለዚህ
በወቅቱ በጣም ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ስለነበርኩ የሰውዬውን ሥም እና
የታርጋ ቁጥር ለመጠየቅ እና ለማወቅ አልሞከርኩም።” ብላ ኒኪ
መለሰችለት፡፡

ጆንሰን በጣም በሚሰረስር አይን እየተመለከታት “ዶክተር አንቺ ምን
አስበሽ ጥቃት ደረሰብኝ ለማለት እንዳመለከትሽ ልንገርሽ? ስለ ላንድክሩዘር መኪናው፣ ስለ ቀዩ ስፖርት መኪና እና ስለ ስፖርት መኪናው ሹፌርም
የተናገርሽው ነገር ሁሉ ፈጠራ ነው እንጂ በፍፁም እውነት አይደለም::”

“ምን አልክ?” ብላ ኒኪ በግርምት አይን ተመለከተችው፡፡

“ባልሽ በህይወት የለም” ብሎ ጆንሰን በማስከተልም “በቃ በጣም ብቻሽን
ነው የምትኖሪው:: ማንም ላንቺ አትኩሮት የለውም፡፡ ስለዚህ የሆነ ሰው የሆነ ተዋጊ ጦሩን እና ጋሻውን ይዞ መጥቶ በመኪና ገጭቶ ሊገድልሽ የመጣ ጥቁር ላንድክሩዘር እና ያዳነሽ ወጣት ባለ ስፖርት መኪና ፈጥረሽ አወራሽ፡፡ ኦ! አይሆንም! ስለዚህም እኛ እንድናምንሽ የሆነ የተሳሳተ ቁጥርን ሰጠሽን!” አላት፡፡

ይህንን የሰማችው ኒኪም ወደ ጉድማን ዞራ “ባልደረባህ አዕምሮው ትክክል አይመስለኝም።” አለችው። ጉድማንም በእሷ ሀሳብ በመስማማት ጆንስን ላይ አፈጠጠበት::

“ይቅርታ ዶ/ር ሮበርትስ” ብሎ ሊቀጥል ሲል ጆንሰን ጣልቃ ገባ እና እንዴ? አስበው እስቲ አንድ የሆነ ጥቁር ላንድክሩዘር መኪና መስታወቱ ወደ
ጠረጴዛውን እየደበደበ “እዚህ ክፍል ውስጥ ዕብድ የሆነ ሰው እኔ ብቻ ነኝ
ምንም አይነት በአደጋው የደረሰባት ቁስል ሳይኖር እናም ደግሞ ማንም ውስጥ የማያሳይ የታርጋ ቁጥሩን የማታውቀው ቀይ የስፖርት መኪና ለዚህ ደረስብኝ ለምትለው ነገር ምስክር መሆን የሚችል ሰው የሌለው::

እንዴ የሆነ የሆረር ፊልም እያወራሽልን ነው እኮ የሚመስለው ዶ/ር ሮበርትስ? ይገርማል! ይደንቃል! እና እኔ አንቺ ላይ ጥቃት ደርሶብሽ ነበር ብዬ እንዳምንሽም ትፈልጊያለሽ? በፍፁም!” አላት ጆንሰን ጥርሱን ነክሶ እንዳፈጠጠባት።

ይሄኔም ኒኪ ከተቀመጠችበት ተፈናጥራ ተነሳች እና የእርሳስ ቀለም ያለውን ቀሚሷን በእጇ እያስተካከለች ወደ ጉድማን ፊቷን መለሰች፡፡

“ይቅርታ መርማሪ ፖሊስ ጉድማን የተለየ ነገር በዚህ ዙሪያ ላይ ካገኛችሁ አሳውቀኝ ወደ ቤት መሄድ አለብኝ። ለዚህ ቂላቂል የህፃናት የሳይኮሎጂ ጨዋታ የሚሆን ጊዜ የለኝም፡፡ የእሱንም ስድብ እዚህ ቁጭ ብዬ ልስማው አልገደድም። መልካም ቀን” አለችው፡፡

መርማሪ ሉው ጉድማንም ይህቺ ሴት ንዴት ያምርባታል ብሎ በውስጡ
እያሰበም በሂል ጫማዋ የምርመራ ክፍሉን ወለል እያንቋቋች ክፍሉን ለቅቃ
ስትወጣ ከኋላዋ ተመለከታት።

ቂላቂል” ብሎ ወደ ሚክ ዞሮ በንዴት እና በግርምት እየተመለከተው

“ይሄ የሰጠችህ ስም ሳይስማማህ አይቀርም ሚክ እህ?” ብሎ ነቆረው፡፡

“ይህቺ ሸርሙጣ ናት!” አለ ጆንሰንም በንዴት እንደተሞላ፡፡

“ሸርሙጣ እና ውሸታም ናት። በዚያ ላይ ደግሞ ጊዜያችንን እያባከነችብን ነው”

ጉድማንም ከተቀመጠበት በንዴት ውስጥ ሆኖ ተነሳ እና “ከዚህች ሴትዮ ጋር ያለህ ነገር ምንድን ነው? ደግሞስ ባለፈው ከጥርጣሬ ነፃ ሆነን እናውራ
ተባብለን አልነበር? ምን ነካህ” ብሎ በቁጣ ጠየቀው።

“እንደዚያ ስለሆነ ነው ነገሩ! ደግሞም የምናገረው የተሰማኝን ነገር ነው።
የሆነች የቀን ቅዠት ውስጥ የምትገኝ ሴት ናት። ማንም ደግሞ እሷን ሊገድል አንዳችም ሙከራ አላደረገም።”

“ስለ ክርስቶስ ብለህ ሚክ! የፎሬንሲክ ምርመራ ማስረጃ እኮ አግኝተናል።” አለው ጉድማን፡፡

“የሆነ መኪና ጎማ የሸርተቴ ምልክቶች? አቦ እነዚህ ነገሮች እኮ እሷ ተሞክሮብኛል ብላ ካመለከተች የግድያ ሙከራ ማረጋገጫ ሊሆኑ እንደማይችሉ አንተም እኔም በደንብ እናውቃለን አይደል?” ብሎ ጆንሰን ገጉድማንን ጠየቀው....

ይቀጥላል
👍1
እሽሙርም የለብኝ

ቅኔም እልተካንኩ

ብዕሬም አልተባ ፣

በይ ቸሩን ያጋጥምሽ

ደጋግ እና የዋህ

ቅን ቅን ቤትሽ ይግባ ::

🔘ሥፍራዬ ጥላዬ🔘
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሀያ_ሦስት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

...“አባ አይቀድሱብኝ። ይልቅ መስቀሉን ወዲያ ያስቀምጠና ልብሶን አወላልቀው አቅፈውኝ ይደሩ፡፡” አላች የለበሰችውን አበሻ ቀሚስ እያወለቀች::

ያወለቀችውን ቀሚስ ከቁም ሳጥኗ ሰቅላ ተመለሰች፡፡ ከሰውነቷ ጋር የተለጠፈ የሚመስለውንና ያፈጠጠ ጡቷን ወጥሮ የያዘውን ነጭ ልስልስ የውስጥ ልብሷን በጭንቅላቷ በኩል እየታገለች ሳበችው:: መካከለኛ የፓፓያ ቅርጽ ያላቸው ጡቶቿ ውስጥ ልብሱ ሟዥቅ አድርጓቸው ሲያልፍ ናትናኤል ዓይን ላይ እንደ ጎማ ደጋግመ ነጠሩበት፡፡ ያልተሟሽ ሸክላ
የመሰለው ደረቷና እንብርቷ ኣካባቢ የሚታየው ቅርጿ ገና ሳይነኩት ከሩቅ
የሚለሰልስ ነው:: የዳሌዋ ማዛን በአግባቡ አበጥ ብሎ የሽንጧን አወራረድ
ደርዝ ይጠብቃል፡፡ ናትናኤል ባለፉት ቀናት እየተላመዳት በመምጣቱ
ዓይናፋርነቱን ከላዩ ላያ ጥሎ ለመጀመሪያ ጊዜ ቄስነቱን ረስቶ ትክ ብሎ ተመለከታት፡፡ አይኖቹን ከሰውነቷ ላይ ወደ ታች ከታች ወደ ላይ አራወጣቸው፡፡ ዞር በል ይሉኝታ... ህሊና በማስተዋል እየታገዘ በውበት አድናቆት ያርካ…ተፈጥሮ ትደነቅ... ከእግዚአብሄር በታች ቅርጽ ቢመለክ ምን ያስገርማል! ....ሴት ልጅ ቅርጽ፤ የጽጌረዳ አበባ ቅርጽ የግራር ዛፍ
ቅርጽ፤ የወንዝ ዳር አለት፤ የንስር አሞራ፤ የእንስሳ ፣የሜዳ አህያ... የዘውዲቱ... እህህ!

“ምነው አባ ቄሱ ትኩር ብለው አዩኝ?” ስትለው ከሄደበት ሃገር ተመለሰ፡፡
“አይ ዝም ብዬ እንደው…. አለ አይደል…” የሚመልስላት ጠፋው፡፡ ትንሽ ደንገጥ እንደማለት ቢልም እይታውን ከላይዋ ላይ አልነቅል አለ፡፡

ዘውዲቱ እየተውረገረገች ወደ ቁም ሳጥኗ ተጠግታ እጇን ወደ ውስጥ ሰድዳ የተሰበረ የፊት መስታወት ስታወጣ ሰ
በጀርባና በትከሻዋ የደሳሳዋን ትንሽ ክፍል የታመቀ አየር የምትቀፈው መሰለች፡፡ : የዳሌዋ ሚዛናዊ እንቅስቃሴ ለመጥ ካለው ቀጭን ወገቧ ጋር ሙዚቃዊ ስልት ፈጥሮ በውስጥ ሱሪ ብቻ የተሸፈነውን መቀመጫዋን ጎልቶ እንዲወጣ አድርጎታል፡፡ናትናኤል ሰውነቱ ሲሟሟቅ ተሰማው፡፡ : ይሄ ነው ብሎ የማይለው ኣንዳች ስሜት ሁለመናውን ይወረውና ደወጣጥረው ጀመር፡፡

“እንዳቅማችን እኛም መስተዋት ኣለን… የተሰበረም ቢሆን የፒያሳም ባይሆን ቅባትም…” አለችና ከአልጋዋ ትራስጌ የቅባት ቆርቆሮና ብልቃጥ አወጣችና ኣልጋው ሳይ እግሪን ኣነባብራ ተቀምጣ ትቀባባ ጀመር፡፡

ኑሮ ካሉት መቃብር ይሞቃል ሲሉ አልሰማሽም? አይዞሽ" አላት ግርንቡዷ ላይ እንደተቀመጠ ዓይኖቹን በተነባበሩት እግሮቿ ላይ ተክሎ የባቶቿን ዘና ያለ ማሪኪ አወራረድ እያደነቀ::

“እሱስ እውነትክን ነው... አትመልከቺ ሱፍ አትዪ መኪና እኛም እንገዛለ ዕድሉ ሲቃና” ብሎ የለ ዘፋኝ" አለች በአሮጌ ማበጠሪያ ፀጉሯን እየሞዠቀች::

ናትናኤል ሳያስበው እንድ የሚጸጽተወ ነገር ድንገት ተናገረ::
“ቆንጆ ነሽ አላት ትንፋሹ እየተናነቀው፡፡ የአድናቆት ቃል ምን ይጎዳል?
“ቆንጆ ነኝ? ቆንጆ ነኝ? አለችና መስተዋቱን አልጋዋ ላይ ውርውር
አድርጋ

“የቄስ ቆንጆስ እንተ...” ብላ ድኩላ እንደሚያጠምድ ነብር ዘላ ተጠመጠመችበት፡፡ ጭኖቿን ጉልበቱ ላይ አጋድማ እያገላበጠች ታሻሽው
ጀመር፡፡

“ልቀቂኝ እለ ሊገፈትራት እየተፍጨረጨረ፡፡
“አሁን ገና ተያዝክ አይደል…” እያለች በሳቅ ትንከተክት ጀመር ፤
ያሞጠሞጠ ጡቶቿን ደረቱ ላይ እንደ ደንገላሳ እያንከባለለች

እንዲህ ነች ዘውዲቱ! ቆንጆ ነሽ እያልክ ደሞ ልትገፈትረኝ፡፡”እጆቿን ሊያስለቅቃት ሞከረ፡፡

“አልለቅህ ዛሬ ብር አምባርህን ሳልሰብረው! …ሙከራዋን ወደ ቀልድ ለወጠች እየተፍነከነከች፡፡
ዝር በይ ዘውዲቱ” በመጨረሻ ተሳከለት፡፡ ሲገፈትራት እጇን አላልታ ለቀቀችውና አልጋዋ ውስጥ ጉብታ እያስካካች ትንፈቀፈቅ ጀመር። ሙከራዋን ቡኋልዮሽ ኣስተሳሰቧ ቀልድ እድርጋ እንዳየችው ለናትናኤል ታውቆታል፡፡

ናትናኤል ሁለመናው እንደጋለ ነው፡፡ አልቦታል፡፡ የልቡ አመታት ጨምሯል፡፡ ቀዝቃዛ ገላዋ ለቆት የሄደ አልመስል እስኪለው ድረስ ተቅበጠበጠ፤ ተቁነጠነጠ፡፡ ሱሪው መወጣጠሩን አሁን ነው ያወቀው። ሠይጣን የሚባለው ለካ ይሄ ነው ኣዳምና ሄዋን ወይስ ሄዋንና ኣዳም አዳም ለካ ደካማ ነው… ኢምንት…. የሴት ትንፋሽ በሙቀት ንረት በቅጽበት
ጉድ የሚያደርገው የሴት ልጅ ገላ ሲነካውና የሴት ልጅ ጣት ሊዳስሰው
በረዶ ቀልጦ በሴኮንዶች ምርኮኛ የሚያደርገው ይገርማል ለካ ሰው ወዶ አይደለም አይገቡበት አዘቅት የሚወርደው በጨለማ ዋሻ ውስጥ የሚሰምጠው ለጥቂት እኮ ነበር፡፡ ለዓላማው የተነሳሳ መሆኑና በኣስተዳደጉ ባይተዋር የሆነበትን ሽርሙጥናን መጥላቱ እንጂ ጉድ ሆኖ ነበር፡፡ ለማናቸውም ግን ፈተና ነው ዛሬ ያሳለፈው። ዘውዲቱም አይበገሬነቱ እንደገባት ግልጽ ነው።

“እረ ና ተኛ ባክህ.…እኔ እንቅልፌ መጣ… መስታወቷን ደሞ እቦታዋ አኑርልኝ፡፡ ጎሽ የኔ ቤት ጠባቂ… የኔ ዘበኛ አለችው እያዛጋች፡፡

“ጭኔ ሳትገባ ታቅፈኛለህ እሺ? በገብርኤል” አለች ቀጠለችና “በሚገባ እንጅ፡፡ ወንድም እህቱን አቅፎ አይተኛም ያለው ማነው?” አላት ፈገግ ብሎ፡፡

ያንን ሌሊት አቅፏት አደረ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ዘውዲቱ ያላትን ሁሉ በገዛችለት በማግስቱ ቦት ጫማን አጥልቆ
ጋቢውን አጣፍቶ ለብሶ ጥምጥሙን ጠምጥሞ፤ መስቀሉን ጉያው ከቶ
ጺሙን አጎፍሮ በምርኩዙ መሬቱን እየተነኮሰ ጭራውን በተን መለስ
እያደረገ ጭንቀትና ፍርሃት እያንጠረጠሩት ወጣ፡፡

“ያመሻሉ እንዴ?” አለችው የቤቷን ተለዋጭ ቀልፍ እየሰጠችው::
“አይመስለኝም፡፡” አላት የተንዘላዘለ ጋቢውን ወደ ትከሻው ሽቅብ
እየሰበሰሰ።

“ተጠንቀቅ... እ... እቤትህ . ድረስ ባትሄድ ጥሩ ነው::ባይሆን ባለቤትህ ከቤት የምትወጣበትን መንገድ ፈልግ፡፡”

“አታስቢ” ብሏት ወጣ፡፡

በጠባቧ ኮረኮንች መንገድ አልፎ ከዋናው የመኪና መንገድ ብቅ እንዳለ ፍርሃት ፍርሃት አለው፡፡ ሰው ሁሉ እሱን እሱን የሚያይ የሚመረምር መሰለው፡፡ ታክሲ ተሳፍሮ ወደፒያሳ ገስጎሰ፡፡ ሂሣቡን ከፍሎ
ከታክሲ ከወረደ በኋላ በመሃል ፒያሳ ሲያልፍ የገዛ ምስሉን በረጃጅሞቹ
የሱቅ መስታወቶች ውስጥ ሲመለከት ለራሱም ማመን አቃተው!ምኑም ቄስ
አልመስልህ አለው:: የሚያውቁት ቢያገኙት…ፈጣሪዬ! አለ ከራሱ ጋር፡፡
አንድ ነገር ደግሞ ይጎለዋል፡፡ ከውጭ የሚታየው አለባበሱ ቅስናው ሕጋዊ
መሆን አለበት። ሕጋዊ የመታወቂያ ወረቀት ያስፈልገዋል፡፡ ምን ማድረግ
እንዳለበት ለሳምንታት አውጥቶ አውርዶ በዝርዝር አቅዶታል፡፡ ጊዜ አላጠፋም መንገዱን ተሻግሮ ከአንድ ፎቶግራፍ ማንሻ ቤት ገባ።

“እንደምን ዋልሽልኝ የኔ ልጅ፡፡” አላት ጠረጴዛ ኋላ ተቀምጣ ትናንሽ ፎቶግራፎች በመቀስ የምትክረክም ሴት ሲያይ፡፡

“አቤት እንደምን ዋሉ፡፡” አለች ልጅቷ ከተቀመጠችበት ተነስታ ቄሱ
ከጉያቸው ያወጡትን መስቀል እየተሳለመች።

“እባክሽ ፎቶ : ልነሳ ብዬ… አሁን ይደርስልኝ ይሆን?' አላት አስተዛዝኖ፡፡

“አዬ… አሁን እንኳን አይደርስሎትም፡፡ ነገ በዚሁ ስዓት ቢመጡ አዘጋጅተን እንጠብቆታለን፡፡”

“እይ! አይ! ነገ በዚህ ሰዓትማ ደብረሊባኖስ አቀበቱ ላይ ነኝ፡፡ አሁን
አልከሽዬ፡፡ እባክሽ የእኔ ልጅ ላስቸግርሽ፡፡ መንገደኛ ሁኜ ነው፡፡”
ለሳምንታት ያጠናውን ቃለ ምልልስ እንዳመጣው፡ እያስተካከለ ያወርደው
ጀመር ቄሱ፡፡ ቀዝቃዛ ፍርሃት ነፍስ ዘርቶ በጀርባው ተንቆረቆረ፡፡

“እስቲ ይቆዩ አንዴ፡፡ አስራት! አስራት!” እያላች ወደ ጓዳ ገባች ልጅቷ፡፡ ብዙም ሳትቆይ ረዘም ጠቆር ያለ ጺማም ወጣት ተከትሏት መጣ፡፡

“እንደምን አለልኝ የእኔ ልጅ::”
👍4
አሉ ቄሱ የተዝረከረክ ጋቢያቸውን ወደትከሻቸው ሰብስበው የእንጨት መስቀላቸውን ወደፊት እየገፉ፡፡

“እንደምን አደሩ።” አላቸው ወጣቱ ጠጋ ብሎ የዘረጉለትን መስቀል እየተሳለመ፡፡

“ተቸግሬ አስቸገርኳችሁ…. ፎቶ ብታደርሱልኝ ብዬ ነበር እባክህ
አሁን ከሰዓት ሂያጅ ነኝ ወደ ደብረሊባኖስ ፎቶ አስፈልጎኝ ነበር መታወቂያዬ ጠፍቶብኝ::” ቄሱ ጺማቸውን እየዳሰሱ እስተዛዝነው ጠየቁት።

“አሁን እንኳን ስራ ነበረብኝ…ብቻ እስቲ ይግቡ፡፡” አለ ወጣቱ፡ ከጀርባ ያለውን ቀያ መጋረጃ እየገለጠ፡፡

“ተባረክ ልጄ… ብሩክ ሁን::”

በርጩማው ላይ ተቀምጠው ቄሱ እገጫቸውን ቀና አደረጉ፡፡ ከግራና ከቀኝ የቆሙት ቡጢ የሚያካክሉ የመብራት እምፖሎች የሚፈነጥቁት ብርሃን ከፊታቸው ላይ ካለው ወዝ ሲያርፍ : ቄሱ
አብለጨለጩ።

“ቀና ቀና ይበሉ አባት… ወደ ጎን…እ…እ… አዎ እዚህ እዚህጋ ይመልከቱ እ….አዎበቃ::” አላቸው መብራቶቹን እያጠፋፋ፡፡

“ተባረክ:: እንጀራህ ከፍ ይበል፡፡” አሉ ቄሱ ከበርጩማው ላይ እየወረዱ፡፡ ተንዘላዝሎ መሬት የደረሰን ጋቢያቸውን መልሰው አጣፍተው ቀዩን መጋረጃ ሰብሰብ አድርገው ወጡ፡፡

“ከይህ ልጠብቅ መሰል፡፡” አሉ ቄሱ ወንበር ላይ ቁጭ እያሉ፡፡
“አዎ፡፡ ቁጭ በሉ! ቁጭ በሉ፡፡” አለቻቸው ወጣቷ ሴት።
“ተባረኬ የኔ ልጅ…ተባረክ፡፡”
ከግማሽ ሰዓት ሰኋላ በትንሽ የወረቀት ከረጢት ውስጥ ስድስት ፎቶግራፎች ይዘው ከፎቶግራፉ ቤት ወጡ፤ ቁና ቁና እየተነፈሱ ቄሱ፡፡

ፎቶግራፍ ብቻውን በቂ አይደለም፡፡ ወረቀቱ ያስፈልጋል፡፡ መታወቂያ ወረቀት፤ የማንም ይሁን ብቻ መታወቂያ ወረቀት፡፡ አንድ ስርዓት አስከባሪ አስቁሞ አባ መታወቂያ ቢለው ሳይፈራ ሳይቸር ደረቱን
ገልብጦ ጋቢውን ጎልቦ መዥረጥ ሊያደርገው የሚችለው መታወቂያ ወረቀት ያስፈልገዋል፡፡ ከየት እንደሚያገኘውም ያውቃል። የመታወቂያ ወረቀቶች እንደዋዛ ጠረጴዛ ላይ ጣል የሚደረጉባቸው ቦታዎች የት የት እንዳሉ
ያስታውሳል፡፡ ባለፉት ሳምንታት ቀን በሃሳብ ተጠፍሮ እየተንጎራደደ ሌሊት
በቅዠት ተወጥሮ እየተወራጨ የተዘጋጀበትን ዕቅድ ተራ በተራ ይፈጽመው ጀመር፡፡

ከመንገድ ጥግ ካሉ ሱቅ የፖስታ ከረጢትና ወረቀት ገዝቶ ወረቀቱን አጣጥፎ ፖስታነው ውስጥ ከቶ ፖስታውን አሸገወና ወደ ዋናው ፖስታ ቤት አመራ፡፡

ረጅም ምርኩዙን ከብበቱ፡ ይዞ በፖስታ ቤቱ የላያ በር ገባ፡፡ የፖስታ ሳጥኖች የተደረደሩበትን መተላለፊያ ኣልፎ ካዋናው ኣዳራሽ ዘው አለ፡፡መደዳውን ከተገጠገጡት መስታወት መስኮቶች ጀርባ የፖስታ ቤቱ ሠራተኞች በየወንበሮቻቸው ላይ ተደርድረው ደንበኞቻቸውን ያስተናግዳሉ፡፡

ወደ ቀኝ ገልመጥ አለና ወደ አንደኛው የደብዳቤ መጻፊያ ወረጴዛ ተጠግቶ ጠረጴዛው ላይ አቀረቀረ፡፡ኣልፎ አልፎ ቀና እያሳ ከፊት ለፊቱ በስተግራ ጥግ ያለውን መስታወት ይመለከት ጀመር፡፡ ልቡ እለቅጥ ተጣደፈበት፡፡ በሃሳቡ ሺህ ጊዜ ያመላለሰው ዕቅድ ሊዘበራረቅበት ዳዳው፡፡

ከመስኮቱ በታች ያለውን ጠረጴዛ ተመለከተ፡፡ ሁለት ይህኑ ሥስት
ብቻ የመታወቂያ ወረቀቶች ይታዩታል፡፡ ካቀረቀረበት ቀና ኣለና በእጁ የያዘው የታሸገ የፖስታ ከረጢት ወደፊት ኣንከርፍፎ ወደ መስኮቱ፡ ተጠጋ፡፡
የደረቀ ከንፈሩን በደረቅ ምላሱ ቦረሽው፡፡

ከፊት ለፊቱ አንድ ሰው ቀደም ብሎ ደረሰና ከመስታወቱ ጀርባ ለተቀመጠችው ወጣት ሴት ሠላምታ ከሰጣት በኋላ አንድ ትንሽ ወረቀት ከኪሱ አውጥቶ አቀበላት፡፡

ልጅቷ ወረቀቷን ተቀብላ ካነበበቻት በኋላ ከተቀመጠችበት ተነስታ ከጀርባ ወዳለ የቁም ሳጥን ሄደች:: የእንጨት ሳጥኑን ከፍታ ኣንዴ ኣንዱን አንዱ ሌላውን ስታነሳ ከቆየች በኋላ አንድ በካኪ ወረቀት የተጠቀለለ ዕቃ ይዛ ተመለሰች::

“ዶክተር ዓለሙ ገዛኸኝ?” አለች ወረቀት ያቀበላትን ሰው ቀና ብላ ተመልክታ፡፡

“አዎ…ነኝ”
“መታወቂያ፡፡”

ሰውየው ቀልጠፍ ብሎ የገንዘብ ቦርሳውን አውጥቶ ከውስጥ
የመታወቂያ ወረቀቱን መዘዘና አቀበላት፡፡ ልጅቷ መታወቂያ ወረቀቱን ተቀብላ የተጸፈውን ስምና ፎቶግራፍ ከተመለከተችና ትክክል መሆኑን
'ካረጋገጠች በኋላ በካኪ ወረቀት የተጠቀለለውን ዕቃ ለሰውየው አቀበለችውና

ይክፈቱት፡፡ አለች

ሰውየው ከውጭ አገር የተላከለትን በካኪ ወረቀት የተጠቀለለ ዕቃ ያለጥንቃቄ ወረቀቱን ከላይ ቀዳዶ ኣንስቶ ተመለከተው የተደራረቡ አራት
የቪዲዩ ክሮች ነበሩ፡፡

“ሳንሱር ኣድርገወት ይመለሱ፡፡ መታወቂያዎ እዚህ .. ይቆያል፡፡
በዚህ ቀጥታ ይሂዱና ወደቀኝ እጥፍ ሲሉ..” ልጅቷ ሰውየውን አመላከተችው፡፡

ሰውየው የተላኩበለትን አራት ክሮች ሰብስቦ ይዞ ከአዳራሹ ወጣ፡፡

“የኔ ልጅ” አሉ ቀረብ ብለው ቆመው የነበሩ ነጭ “ጥምጥም የጠመጠመ ቄስ፡፡ “እዚህ ላይ የሚጣፈውን ትጥፊልኝ አላወቅበት ብዬ እንዳላዟዙረው ሰጋሁ::” የያዘኑን የታሸገ ፖስታ ወደ ልጅቷ ፊት
አስጠጉት፡፡ ሲናገሩ ድምጻቸው ይንቀጠቀጣል፡፡ ወረቀቱን ሲያቀበሏት
ምርኩዛቸው አምልጧቸው ወደቁ፡፡

“ምንድነው የፈለጉት?” እለች ልጅቷ ቄሱ ሲደነጋገሩባት ግራ ተጋብታ፡፡

💫ይቀጥላል💫
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሀያ_አራት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ


..... “የኔ ልጅ” አሉ ቀረብ ብለው ቆመው የነበሩ ነጭ “ጥምጥም የጠመጠሙ ቄስ፡፡ “እዚህ ላይ የሚጣፈውን ትጥፊልኝ… አላወቅበት ብዬ
እንዳላዟዙረው ሰጋሁ::” የያዙትን የታሸገ ፖስታ ወደ ልጅቷ ፊት አስጠጉት፡፡ ሲናገሩ ድምጻቸው ይንቀጠቀጣል፡፡ ወረቀቱን ሲያቀበሏት ምርኩዛቸው አምልጧቸው ወደቁ፡፡

“ምንድነው የፈለጉት?” እለች ልጅቷ ቄሱ ሲደነጋገሩባት ግራ ተጋብታ፡፡

“የኔ ልጅ ይህን ቦስጣ ልልከው ፈልጌ ነበር፡፡ ታዲያ ከይህና ከይህ የሚጣፈውን እንዳላበላሽ አሉ ቄሱ ያሽጉትን ፖስታ እያገላበጠ፡፡ “እምን ከምን እንደሚሰፍር አላውቅት ብዬ ትጥፈልኝ፡፡” ለሳምንታት
የሸመደዱትን ተረተሩላት።

“የሚልኩለትን ሰው አድራሻ ያውቁታል?” አለች ልጅቷ ፖስታውን ልትቀበል እጁን እየዘረጋች::

“እንዴታ ቄስ ገብረክርስቶስ ጋ”
“አይደለም… አይደለም… ማለቴ ሙሉ አድራሻውን” አለች ልጅቷ ፈገግ ብላ፡፡

“እነግርሻለሁ፡፡ ብቻ እንቺ ከሥፍራ ከስፍራው ጣፊልኝ::”
ልጅቷ ወረቀቱን ከተቀበለቻቸው በኋላ ወረቀቱ ላይ አቀርቅራ የሚነግራትን ለመፃፍ ትጠባበቅ ጀመር።

“ቄስ ገበዝ ገብረክርስቶስ በይማ::”

ልጅቷ በፖስታ ከረጢቱ ጀርባ ላይ ቄሱ ያሏትን ማስፈር ጀመረች፡፡ ቄሱ ጠጋ ብለው ከጠረጴዛው ላይ ተደራርበው የተቀመጡትን የመታወቂያ ወረቀቶች ሰብሰብ ስብራብ አደረጓቸው፡፡

“እንዲያ ደብረሊባኖስ ገዳም በይ አዎ..ደብረ…” ቄሱ ከጠረጴዛው ላይ የሰበሰቧቸውን አራት መታወቂያች አጋብሰወ ከጋቢያቸው ስር ከኪሳቸው ውስጥ ጨመሯቸው። “ሸዋ... በይበት... እንዲያ ተባረኪ!” አሉ ድምጻቸው እየተንቀጠቀጠ፡፡

“የእርሶስ አድራሻ? ” አለች ልጅ:: ቀና ብላ እየተመለከተቻቸው፡፡እኔማ ምን አድራሻ አለኝ? መንገደኛም አደለሁ?” አሏት ቄሱ
ፖስታቸውን ተቀብለው ለመሄድ እየተጣደፉ፡፡

“ቢሆንም ስሞትን እንኳን ልጻፈው፡፡”
“ልክ! ልክ! ቄስ ዘነበ ዘነበ ወልደሰማያት በይልኝ፡፡ አንዲያ ዘነበ፡፡” አሉ ድንገት የተቻኮሉት ቄስ፡፡

የፈለጉትን አድራሻ በታሸገው ፖስታ ላይ ጽፋ እንደጨረሰች ቄስ መርቀዋት ፈጠን ብለው ከፖስታ ቤቱ አዳራሽ ወጡ፡፡ ገልመጥ አላሉም፡፡መንገዱን ተሻግረው ታክሲ ውስጥ ገብተው ወደ ክፍለሃገር አውቶብስ መሳፈሪያ ሲያምሩ ነበር ምርኩዛቸውን ረስተው መምጣታቸው
የታወሳቸው፡፡ ክው አሉ፡፡ ለመመለስ ግን አልደፈሩም::
ናትናኤል የገጠር አውቶቡስ መሳፈሪያ ደርሶ እንደወረደ ወደ ተከራየው ወደ ዘውዲቱ ቤት አልሄደም፡፡ ወደ አንድ ሱቅ ገባና ስልክ ጠይቆ ርብቃ መሥሪያ ቤት ደወለ፡፡

ሃሎ ምህረት?”
“ናትናኤል!” አለች ምህረት ገና ድምፁን ስትለየው፡፡
“እንደምንድነሽ ምህረት ደህና ነሽ?”
“አንተ! ምን እንዲህ አጠፋህ? በጤናህ ነው?”
“አለሁ እለሁ፡፡ ምህረት እባክሽ ርብቃን ትጠሪልኝ…”
“የለችም፡፡ ለመሆኑ አዲስ አበባ ነው ያለኸው?”
“ስራ ኣልገባችም?” አለ ጥያቄዋን ችላ ብሎ፡፡
አዎ ከትላንት ጀምራ አልገባችም፡፡ ቤቷ ደውዬ ነበር የሚያነሳ የለም:: ደጋግሜ ሞክሬ ነበር፡፡”
ናትናኤል ምህረትን ተሰናብቶ ስልኩን ዘግቶ ወደ ዘውዲቱ ቤት መንገድ ጀመረ፡፡ ሃሳብ ገባው፡፡ አሟት ይሆን? እንዴት ሁለት ቀን በተከታታይ ከሥራ ትቀራለች.… በጤና ብትሆን? ቤቷ ሊደውል አሰበና ፈራ ስልኳ ተጠልፎ እንደሆንስ ድጋሚ አደጋ ላይ ሊጥላት አይገባም:: ቆያይቶ ሰሞኑን እዚያው ምህረት ቢሮ ደውሎ ቢያነጋግራት ይሻላል፡፡

ናትናኤል ዘውዲቱ ቤት ሲደርስ በሩ እንደተቆለፈ ነበር፡፡ ዘውዲቱ የለችም ማለት ነው፡፡ የሰጠችውን ተለዋጭ ቁልፍ አውጥቶ በሩን ከፍቶ ገባና ከውስጥ ቆለፈው:: ወዲያ ጋቢውን ወርውሮ ጥምጥሙን አውልቆ ጥሎ ከኪሱ ውስጥ ከፖስታ ቤት የሰረቃቸውን አራት የመታወቂያ ወረቀቶች አወጣና ተራ በተራ እየከፈተ አነበባቸው፡፡

ሻለቃ ብርሃኑ ገብረማርያም አቶ ጀማል አብዱልከሪም ዶክተር አለሙ ገዛኸኝ ሲስተር ሠናይት አሽኔ፡፡ ሀሳብ ገባው የትኛውን ሊያቀስ እንደሚችል ግራ ገባው::

ምርጫ አልነበረውም፡፡ዶክተር አለሙ ገዛኸኝ የሚለውን መታወቂያ ነጥሎ አንስቶ በጥንቃቄ ፎቶግራፉን ነቀለና ቀን ከተነሳቸው ፎቶግራፎች መሃል አንዱን ተካበት፡፡ ወዲያው ቶሎ ብሎ ከመሬት አንስቶት ወደ ቤት ገባና ጭቃውን በጨርቅ ያፀዳ ጀመር፡፡ የመታወቂያ ወረቀቱን በጥንቃቄ ጠራረገው፧ አፀዳው፡፡እንደ በፊቱ ንፁህ ባይሆንም..መቼስ.….አለሙ ገዛኸኝ የሚለው ይነበባል፡፡ያንን ነበር የሚፈልገው:: 'ዶክተር የሚለው አስፈላጊ አልነበረም፡፡ ለተቀሩት መታወቂያዎች ደግሞ ሰኑን ሌሎች ፎቶግራፎች ይነሳላቸዋል፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በሩ..የመኝታ ቤቷ በር ወደ ውስጥ ሲገፋ ጠረጴዛውን ደገፉ እንዳለች ቀረች፡፡በሩ ተከፍቶ የሰው ቅርጽ ታያት፡፡ ሰውየው ወደ ውስጥ ገብቶ በሩን ዘጋው፡፡ ከጀርባው ባለው መስኮት የሚገባው ስስ የጨረቃ
ብርሃን ቀጠን ረዘም ካለው ሰውነቱ ላይ ሲያርፍ ሰው ሳይሆን ህይወት ያለው ጥላ መሰላት፡፡ ግራ ጉንጩን ከላይ እስከታች የገመሰው ኣስጠሊታ ጠባሳ የአካሉ አንድ ክፍል እንዳልሆነ ሁሉ በጨረቃዋ ብርሃን ውስጥ ጎልቶ ታያት፡፡ አተኩራ ትናንሽ አይኖቹን ተመለከተቻቸው፡፡ ሰውነቷ ይንቀጠቀጥ ጀመር፡፡ ሆዷ ውስጥ ያለው ሽል የተላወሰ መሰላት ሊያስመልሳት እንደፈለገ ሁሉ አንጀቷ ሲመናተቀል ለራሱ ነፍስ የዘራ ይመስል ሲቋጠር ሲፈታ.. ሳይታወቃት ወደፊት ዘላ ጉብ አለችበት፡፡

“ገደላችሁት! ገደላችሁት አይደል?

አታለላችሁኝ!” አውቃ አስባ ሳይሆን ከውስጥ የሚነዳትና የሚጋልባት ዛር እንዳለ ሁሉ ዘላ ፀጉሩን ጨመደደችው፡፡ ፊቱን በጥፍሮቿ ገባችበት::

“ርብቃ!” ጥፍሮቿን አሹላ አይኖቹን ልትጓጉጠው ስታሻቅብ ባለ በሌለ ሃይሉ እራሱን እየተከላከለ ጮኸ፡፡ “ርብቃ! አልገደልነውም! ማንም አልደረሰበትም... እሱን ለመግደልም አላሰብንም... ርብቃ አዳምጪኝ!” ሁለት እጆቿን ወደኋላ ጠምዝዞ ደረቷን ደረቱ ላይ ለጥፎ አገጯን በቀኝ እጁ ግጥም አድርጎ ይዞ ጮኸባት፡፡

“ውሽታም! ውሸታም! አታላችሁኛል፤ ገድላችሁታል.…ቱፍ” ፊቱን በምራቅ አለበሰችው::

“አልሞተም አለ፡፡ ስላመለጠን ነው ወደ አንቺ የመጣነው:: ርብቃ ረጋ በይ!”
ለአንድ አፍታ ረጋ ያለች መሰሰች፡፡ቀና እንዳለች ቁና ቁና እየተነፈሰች አፈጠጠችበት:: ድንገት ፡ እጆቿን መንጭቃ ከእቅፉ ወጣች፡፡ ከፊቱ ተጋርጦ አይኖቿን አጉረጠረጠችበት፡፡

“ልትገድሉት ነበር የጠራችሁት፥ ጓደኛውን እንደገደላችሁት እሱንም ልትገድሉት ነበር፡፡ አትዋሽ! አሁን ደግሞ ወር ሙሉ እናገኘዋለን ታገሽ ስትለኝ ቆይተህ አመለጠን ትለኛለህ! ”

“ርብቃ እመኝኝ፡፡ እሱን የመግደል ሃሳብ አልነበረንም፡፡ አስፈላጊም አልነበረም:: ምንም አያውቅም፡፡ በድንግዝግዝ ጨረቃ ብቻውን እንደሚሮጥ እብድ ነው::” አለ ሰውየው ከኪሱ ወስጥ መሃረብ አውጥቶ ፊቱ ላይ የትዝረበረበውን ምራቅ እየጠረገ፡፡

“ጓደኛውን አልገደላችሁትም? አትዋሽ!”

“ገድለነዋል፡፡ አስፈላጊም ነበር መሞቱ:: ምሥጢሩን ከሞላ ጎደል ደርሶበታል፡፡ በማንኛውም ሰዓት ሊያወጣው ይችል ነበር፡፡ ኣደገኛ ሰው ነበር፡፡

“እሱን የገደላችሁት ሌሊት ናትናኤልን ጠርታችሁታል:: ልትገድሉት ነበር፡፡ አትዋሽ!” ከሥሯ ያለውን ወለል በእግሯ ደቃችው፡፡

“ርብቃ እመኝኝ፡፡ የዛን ቀን ጓደኛው አደገኛ የሆነ እርምጃ ወሰደ፡፡ገደልነው:: ምንም ምርጫ አልነበረም... እርግጥ በጥድፊያ ውስጥ ነበርን የዛን ማታ ሁለቱም እንዲገደሉ ነበር የተላለፈው ትዕዛዝ፡፡ እንደ አጋጣሚ ያንቺ ሰውዬ አመለጠ.. ትራፊክ ፖሊስ
👍2
ይዞት፡ በማግስቱ ግን ሁኔታው ሲረጋጋ የሞቱ ትዕዛዝ ተነስቶ የሃያ አራት ሰዓት ክትትል እንዲደረግበት
ነበር የተወሰነው፡፡“

“…ሰዎቻችን መሥሪያ ቤቱ ሲገባ አይተውታል፡፡ ግን ከሰዓት በኋላ
እንደደወለለሽና አምባሳደር ቲያትር ውስጥ በስውር ሊያገኝሽ እንደሚፈልግ
ባሳወቅሽን ጊዜ ሰዎች ተመድበው ትያትር ቤት ድረስ ተከታትለውሽ ነበር ግን አንቺ ራስሽ ከመታጠብያ ቤት ከወጣሽ በኋላ እንደተሰወርሽበት ነበር ሪፖርት ያደረገው ከዛ በኋላ ልናገኘው አልቻልንም

“ብታገኘት ምን ልታደርጉት? ልታርዱት፤ ልትገድሉት?”
“ረጋ በይ፡፡ ማንም ሊገድለው የሚፈልግ የለም፡፡”

“ታዲያ ለምን ፈለጋችሁት?” ፊቷን አስግጋ ቀረበችው፡፡ “ተናገር ምን ልታደርጉት ፈለጋችሁት? ሁሉን ዘርዝረህ ንገረኝ ናትናኤል ከመጥፋቱ በፊት አንድ የተሰወረ ዲፕሎማት እንደሚፈልግ ነግሮኛል፡፡ ምን ማለት ነው? ማነው እሱ?

"ሃገርኩሽ! ለሞት የሚያደርሰው ነገር የለም ፤ በቃ፡፡ ምንም አያውቅም የተሰባበሩ ጥቃቅን ጥያቄዎች ይዞ ነው ከወዲያ ወዲህ የሚሮጠው:: እርግጥ ጓደኛው ስለታገደለ ፈርቶ ይሆናል... ግን ባጭሩ እሱን መግደል አስፈላጊ አይደለም:: በቁጥጥር ስር ልናቆየው ነው የምንፈልገው... እስከጊዜው:: ከዚህ ውጪ ዝርዝር ነገሮችን ልነግርሽ አልችልም፡፡ አንቺም ታውቂያለሽ እያንዳንዳችን ማወቅ የሚባን እንደየደረጃችንና እንደአስፈላጊነቱ
ማወቅ የሚገባንን ብቻ ነው::”

“ልታስሩት!…የፊጥኝ አስራችሁ እየገረፋችሁ እያንገላታችሁ ልትገድሉት” አይኖቿን አጥብባ በጥላቻ ተመለከተችው፡፡ ለዚህ ነው
የፈለጋችሁት እንግዳው!”

“ዓላማ አለን! አስፈላጊ ከሆን ደግሞ ሌሎችን ማስወገድ ብቻ ሳይሆን የገዛ ሕይወታችንን አሳልፈን ልንሰጥለት የተዘጋጀንለት ዓላማ አለን!”

“ዓላማ ቢስ ናችሁ አታላችሁኛል! ሁላችን ተታለናል፡፡ ምንም ቁንጅና የለንም፡፡ ቆንጆዎች አይደላችሁም! ነፍሰ ገዳዮች ናችሁ!”

“ቆንጆ ማለት ደካማ ማለት አይደለም.… ቆንጆ ማለት አቅም የለሽ ማለት አይደለም… ራሱን የማይከላክል ቁንጅና የቀትር ፀሃይ ሲወጣ ይረግፋል…ቆንጆዎች ነን… ጠንካሮችም ነን፡፡”

በምን ተለያችሁ ከቀድሞዎቹ?..በምን“ ታለያችሁ ከከዳተኞቹ?... ሥልጣን ላይ ከተሰገሰጉት እሾሆች በምን ተለያችሁ? እናንተም እንደነሱ ትኮሰኩሳላችሁ፤ እናንተም እንደነሱ ትናደፋላችሁ፤ እናንተም እንደነሱ እሾህ ናችሁ! ምኑ ላይ ነው ቁንጅናችሁ?”

“ቁልቋልም ጽጌረዳም እሾህ አላቸው.…ሁለቱም ይናደፋሉ:… ጽጌረዳ ግን ቆንጆ ነው ጽጌረዳዎች ነን… ጥቋቁር ጽጌረዳዎች... ጠላቶቻችንን ሊቀጥፉን የሚመጡትን እንደ ጽጌረዳ እንናደፋለን... ለሚያደንቀን ግን ውብ ነን ለሚያሽቱን ጥዑም ነን፡፡”

ፊቷን መልሳ አልጋዋ ላይ ቁጭ አለች፡፡

“ቆንጆ ማለት ደካማ ማለት አይደለም…ራሱን የማያከላከል ቁንጅና...” የሚለው የማርቆስ ንግግር ጆሮዋ ላይ ደወለባት፡፡ እነዚህ ምን ቆንጆዎች ናቸው?…በግድያ የሚያምኑ በአፈና የሰለጠኑ የቀትር
ጅቦች ምናቸው ይታመናል? የሠላም ፀሮች!.…ጥላቻዋ ገኖ ይታያት ጀመር፡፡
መቼ ነበር. አዎ ሶስና ለልደት የጋበዘቻቸው ዕለት…. ናትናኤልንና እሷን
“የአፍሪካ ጥያቄ የፖለቲካ ጥያቄ ነው፤ የአፍሪካ ነፃነት የሚገኘው በተዋህዶ
እንቅስቃሴ አፍሪካ አንድ ስትሆን ነው” ባለችው ጊዜ ናትናኤል ምን ነበር
ያላት?ለማስታወስ ሞከረች፡፡ “በአገሮች መካከል ኢኮኖሚያዊ ትብብርና ጥንካሬ መቅደም አለበት፡፡ የፖለቲካው ውህደት ከዚያ በኋላ ነው የሚመጣው... ለአፍሪካ እድገት ቅንጅት ያለው እንቅስቃሴ መኖር አስፈላጊም ሲሆን ሂደቱ ዲሞክራሲያዊ መሆን አለበት፡፡ በዕቅድ የሚመራ ዲሞክራሲ በትምህርትና በልምድ ሊዳብር ይገባል…” ሲል ናትናኤል የተናገራት ትዝ አላት፡፡ ርብቃ አንዳች አዲስ ነገር ህሊናዎ ጓዳ ውልብ አለባት። ይህ ምን ማለት ነው? ናትናኤል ዲሞክራሲያዊ ህብረት ሲል ምን ማለቱ ነበር? አዎን ግልጽ ነው እነዚህ ራሳቸውን “ቆንጆ” ያሉት ሰዎች የሚከተሉት መስመር ይሄ አይደለም፡፡ “እነሱ የሚያምኑት በኃይል ነው:: ዲሞክራሲ ማለት ለነሱ ዝም ብሎ ለአፍሪካ መቆርቆር ነው.. አፍሪካ አንድ ትሁን ሲሉ በኃይል እንጠቀም ማለታቸው መሆኑ በእኩይ ተግባራቸው ይታያል…አይሆንም
አይሆንም ልክ አይደሉም ወይ ናትናኤል...ናቲ ናቲ… ልክ ነህ.. ናቲ…” በእጆቿ ራሷን ቀብራ በሃሳብ ጭልጥ ካለችበት ስትመለስ የግንዛቤዋ
የቀስ በቀስ ሂደት መከለት ስሜቷን ነካው፡፡ ጩሂ ጩሂ አሰኛት፡፡

“ረጋ ብለሽ ኣዳምጪኝ እንዳልኩሽ ልንጎዳው አንፈልግም… ግን ደግሞ በደመነፍስ ያለዕውቀት ጥፋት ለማድረስ ሲሯሯጥ ዝም ብለን ልንመለከተው ኣይገባም… የያዝነውን ዓላማ ስላልተረዳ ብቻ ጠላታችን ሆኗል..

“አስሬ ይሆናል የነገርኳችሁ..በየሳምንቱ በምጽፈው ሪፖርት ላይ.. ይመልመል ብቁ ነው ይመልመል ብያችኋለሁ!” “ርብቃ ያንን አላውቅም… ውሳኔ የሚሰጡ ሌሎች ናቸው… ዋናው ነገር አሁን ባለማወቅ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል…ንገሪኝ..የት ነው ያለው?”

“አላውቅም፤እየፈለግነው ነው የምትለኝ ውሸት ነበር ማለት ነው?እየደወልኩ ጠፋ ስልህ አላመንክኝም ማለት ነው?”

“ውሸትሽን ነው፡፡”
“አላውቅም አልኩሀ ኣላውቅም! ውሸቴን አይደለም፡፡”
“አስታውሽ.…ከናትናኤል ጋር ያገናኘሽ የእኛ ዓላማ ነው:: አንቺ ግን አላማሽን ረስተሽ ለስጋ ፍላጎትሽ ተሽነፍሽ…” አይኖቹን አሳንሶ በንቀት ቁልቁል ተመለከታት፡፡ “የት ነው ያለው...ንገሪኝ፡፡”

“ዓላማችሁ ነፍስ መቅጠፍ መሆኑን ባውቅ ኖሮ፤ አላማችሁ ሕይወት ማጨለም መሆኑን ባውቅ ኖሮ አላማዬ ብዬ አልይዘውም ነበር:”

“ምንድን ነበር የጠበቅሽው? ፌሽታ? ጭፈራ?..አትሞኝ.… ከግባችን ለመድረስ የግድ ደም መፍሰስ ካለበት ይፈሳል…ምርጫ የለንም።” አጠገቧ አልጋዋ ላይ ተቀምጦ ትከሻዋን በሁለት እጆቹ ይዞ ትክ ብሎ ተመለከታት
“...አስታውሽ የጋናው ነቢይ ያለውን፡፡ ደህንነታችን አንድነታችን ነ ከዚያ ውጪ ደህንነት የለንም፡፡ በዚህ ሰዓት ከዓላማሽ ማፈግፈግ አትችይም ክህደት ነው፡፡”

ቀና ብላ አትኩራ ተመለከተችው፡፡

“…እመኚኝ አንጎዳውም… ጊዜው ደርሷል… ያኔ ነፃ ይሆናል፡፡ ለትንሽ ጊዜ አንድ ቦታ ሰውረን እናስቀምጠዋለን… ምንም አናደርገውም…የት ነው ያለው?”

ነገርኩህ'ኮ እኔ ራሴ የት እንዳለ አላውቅም::”
““እደውልልሻለሁ ማለቱን
አስታውቀሽ ነበር፡፡”
“አዎ። ብሎኝ ነበር ግን አልደወለልኝም፡፡”
“ለምን? እንዴት አልደወለም? ምሥጢሩን እውጥተሻል ማለት ነው፡፡”

“ባወጣሁት በነገርኩት ደስ ባለኝ ነበር!” አለችው በጥላቻ እየተመለከተችው፡፡

“እርጉዝ ነሽ? ድንገት ጠየቃት፡፡ ቃናው ጥያቄ ሳይሆን ትዝብት መሰላት

ደነገጠች፡፡ እንዴት ደረሱበት?
“ያ የግል ጉዳዬ ነው።” አለች በትቻላት ድፍረቷን አሰባስባ ኣፍጥጣ
እየተመለከተችው፡፡

“የመጨረሻ ዕድል እሰጥሻለሁ፡፡የት ነው ያለው?”
“ኣላውቅም!”

ድንገት ከትከሻው እንደ ወስፈንጠር ተለጠጠባት። ከአልጋው ላይ
ተፈናጥሮ ተነሳ።ጥርሱን ሲነክስ ጉንጩ ላይ የተጋደመው ጠባሳ በጨረቃዋ
ብርሃን ጎልቶ ወጣ፡፡ ራመድ ብሎ ወደ መስኮቱ ሄደና መጋረጃውን ሰብሰብ
አድርጎ ከአፓርታማው አጥር ውጭ ወደቆመችው ሲትሮይን ቁልቁል
ተመለከተ፡፡ ወዲያው ከግራ የደረት ኪሱ የቅርብ ርቀት መገናኛ ሬዲዮ …
አውጥቶ ተጫነው-

“ቆንጆዎቹ…ቆንጆዎቹ… ዜሮ አራት መቀጠል ትችላለህ።” ፊቱን መልሶ ቀጨለማው ውስጥ አፍጥጦ ተመለከታት፡፡
“ከዳተኛ ነሽ ባንዲ…” አለ ቅዝቅዝ ብሎ፡፡

ከተቀመጠችበት ሳትንቀሳቀስ በፍርሃት ተመለከተችው።

“…ከአሁኗ ደቂቃ ጀምሮ ከዚች ክፍል
መውጣት አትችይም…ሰውዬሽን..አታስቢ እናገኘዋለን፡፡ እንዳገኘነው እናስወግደዋለን፡፡” ወደ መኝታ ቤቷ በር ራመድ ብሎ በሩን ከውስጥ ቀረቀረው፡፡

“ምን ልታደርጉኝ ነው? አኔንም ልትገድሉኝ አሰባችሁ እንዴ?” አለችወ ፍርሃቷን ለመሽፈን እየታገለች።

“አስፈላጊ አይደለም፡፡ አንቺም ታውቂዋለሽ፡፡ አስፈላጊ መግደል ብቻ ሳይሆን በደስታ የገዛ ሕይወታችንን
እንሰዋለን ከአሁን ወድያ በዓለም ላይ ማንም አይመልሰንም! ማንም አይቋቋመንም! ተንቀን፤ ተጠልተን፤ ተዋርደን፤ ለባርነት መለያ ሆነን ኖረናል፡፡ ተግዘናል፤ ተሸጠናል፤ ተለውጠናል፡፡ አሁን ግን ያበቃል፡፡ ደህንነታችንን፤ ለይስሙላ
ያልሆነ አውነተኛ ነፃነታችንን በእንድነታችን እናገኘዋለን ቅርብ ነው ጊዜው…”

ወንበር ስቦ ተቀመጠ፡፡

አልጋዋ ላይ እንደተቀመጠች በጨለማው ውስጥ ኣፈጠጠችበት፡፡ያለፈው ሁሉ እንደቅዠት እየተዘበራረቀና እየተደራረበ መጣባት…

💫ይቀጥላል💫
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_ሀያ


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

...ለምንድነው እሷ የሌሎችን ፈጠራ የምትነግረን?” ብሎ ጉድማን እጆቹን
እያወናጨፈ “ ለምን?” ብሎ ጠየቀው፡፡

ጆንሰንም ትከሻውን ሰብቆ “ምናልባት ትኩረት ለማግኘት ፈልጋ!”

እኮ ያንተን ትኩረት? ላስቀይምህ አይደለም ኒኪ፤ ግን እሷ አንተ ላይ
ምንም አይነት ፍላጎት የላትም”

“አላውቅም ሉው። ምናልባት ያንተን ትኩረት ፈልጋ ይሆናል” አለ እና ማክ በንዴት ስሜት ውስጥ እንደሆነም “ምናልባት እሷን ባገኘናት ቁጥር
የምላስህን በምኞት ማለክለክ እና ሱሪህ ላይ ድንኳን የሚሰራውን ብልትህን
በቅርበት ማየት ፈልጋ ይሆናላ።” ብሎ መለሰለት፡፡

ጉድማንም ራሱን በሀዘኔታ ነቀነቀና በውስጡ እንዴ ይሄ ሰው? ምናልባት ገና የሦስተኛ ክፍል ተማሪ ይሆን?' አለ በሆዱ፡፡

በዚህ የጆንሰን ሙግት የደከመው ጉድማንም ከባልደረባው ጋር ከዚህ
በላይ ቢከራከር ምንም ለውጥ እንደማያመጣ ስላወቀ የምርመራ ክፍሉ
ውስጥ ዝም ብሎ ቁጭ አለ። የባልደረባውን ዝምታ ውይይታቸው እንዳበቃ እንደሚያሳየው ምልክት በመቁጠርም ጆንስን “በብራንዶን ግሮልሽ ላይ የተለየ መረጃን አግኝተሃል?” ብሎ ጠየቀው፡፡

“ምንም የሚጠቅም ነገር አላገኘሁም” ብሎ ጉድማን በመቀጠልም “ራሄል
ኬስሊ የተባለችውን ለቫለንቲና የብራንዶን ግሮልሽን ብዙ አደንዛዥ ዕፅ በመውሰዱ ምክንያት መሞቱን የሚገልፅ ደብዳቤን የፃፈችውን ልጅ ተከታትዬ ለማግኘት ችዬ ነበር”

“እና?”

“ኡፍ” ብሎ ጉድማን በረዥሙ ተነፈሰ እና “ከስምንት ሳምንት በፊት በብዛት ዕፅ በመውሰዷ ምክንያት በሃያ ሁለት ዓመቷ ህይወቷ አልፏል። ቤተሰቦቿም ሳንድያጎ አቅራብያ ነው የቀበሯት።” አለው፡፡

ጆንሰንም በሰማው ነገር ተናድዶ “እነዚህ ልጆች ላይ ምንድነው እየተከሰተ ያለው?” ብሎ በቁጣ ጠየቀ፡፡

“በእርግጥ ያሳዝናል” አለው ጉድማን፡፡

ጆንስን ወደ ቅድሙ ስሜቱ በድንገት በመመለስ “እንዴት እንደሆነ ባይገባኝም
“ኒኪ ሮበርትስ በሁለቱ ግድያዎች ላይ እጇ እንዳለበት ይሰማኛል።” ብሎ
እርግጠኛ ነኝ፡፡ በቃ እውነቱን ለማጣራት በጣም ማረጋገጫው ከእጃችን እያመለጠን ያለ ነው የሚመስለኝ፡፡” አለው ጆንሰን፡፡

ጉድማን ባልደረባው ጆንሰን ልንደርስበት ጥቂት ርቀት ብቻ ነው የቀረኝ የሚለው አነጋገሩን ምንም አይሰማውም። ከዚያ ይልቅ ባልደረባው ዶክተር ኒኪ
ሮበርትስን እና ማዋረዱን ቢተው እሷ
የምትሰጣቸውን መረጃዎች (ለምሳሌ የቀዩ መኪና ሹፌርን ነገር የመሳሰሉ
ጥሬ መረጃዎችን በደንብ ልትገልፃቸው እንደምትችል ይሰማዋል።
እንግዲያውስ ብራንዶን ግሮልሽ የእውነትም ሞቶ ከሆነ የሚቀራቸው ብቸኛ የግድያ ወንጀሉ ተጠርጣሪ የጥቁሯ ላንድክሩዘር ሹፌር ይሆናል ማለት
ነው።

“እሺ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ?” አላት ሀዶን ፊቱ በፈገግታ እንደተሞላ
ከጠረጴዛው ባሻገር የምትገኘውን ኒኪ ሮበርትስን እየተመለከተ፡፡ የትሬይን
ሞት ሊያረዳት ቤቷ ከመጣ በኋላ ተገናኝተው አያውቁም። ዛሬ ላይ ደግሞ
ያኔ የትሬይን ሞት ሲያረዳት ይታይባት የነበረው የሀዘን እና የባዶነት ስሜት
አሁን አይታይባትም።

“ጠይቀኝ” አለችው ኒኪ፡፡

ሀዶንም አይኑን እሷ ፊት ላይ እንደተከለ “የሜየር ሌመን ማለት ምን ማለት ነው?

ኒኪ በሀዶን ጥያቄ ሳቀች። የሚገኙት ሎስ አንጀለስ ቬነስ ውስጥ አቦት
ኬንሌይ መንደር ዳር ምርጥ ምግብ ከሚቀርብበት አዲስ ትንሽዬ ምግብ ቤት
ውስጥ ነው።

ሀዶን በመቀጠልም “እዚህ የምግብ ሜኖዎች ላይ የማያቸው የምግብ
ዝርዝሮች አዳዲስ እና አስደንጋጭ ናቸው። የድሮዎቹ የምግብ ስያሜዎች
የት ጠፉ?”

“ኧረ አሉ” ኒኪ በእንፋሎት የተጠበሰውን ሶሪትን በቢላዋ በስሱ ቆርጣ እና በሹካ ወደ አፏ እየላከች “ከዚህ ስድስት ብሎኮች አለፍ ብሎ ከሚገኘው ኤል ፓሎ ከሚባለው ምግብ ቤት ውስጥ ታገኛቸዋለህ፡፡ ያውም ከዚህ በአስር
እጥፍ ባነሱ ዋጋዎች፡፡ ግን ያው እንደዚህ አይነት ረከስ ያሉ ምግብ ቤቶች
መመገብ ያንተ ስታይል አይደለም ብዬ ነው እዚህ ይዤህ የመጣሁት” ብላ
ነገረችው፡፡

ሀዶን ልክ እንደ በፊቱ ከዶውግ የመኪና አደጋ በፊት ኒኪ እንደዚህ ዘና ብላ ስትተርበው በማየቱ ደስ አለው:: ከባሏ ዶውግ ሞት በኋላ ውስጧ ግማሹ ሀዘን፣ ግማሹ ደግሞ ንዴት እንደሆነ ይሰማዋል። በተለይ ደግሞ ባሏ
በሞተበት ጊዜ ላይ ባወቀችው የእሱ ሚስጥር ባሏን እንደማታውቀው አይነት
ስሜት እንደሚስማት ይገምታል።

“ዲዘርት እንዲቀርብልሽ ትፈልጊያለሽ?” ብሎ ሀዶን ቀዩን የክሬይ ዓሳን
(ከሜይር ሌመን ጋር) በልቶ እየጨረሰ “ወይስ እንሂድ?” ብሎ ጠየቃት፡፡

“ብንሄድ ይሻላል።” ምክንያቱም አሁን ሀቸኮሌት የመብላት ስሜት ውስጥ
አልገኝም።” ብላ መለሰችለት።

እሱ እና ባሏ ዶውግ ባለፉት ስምንት ዓመታት ሊከፍቱት ያስቡት ወደ
ነበረው የቬኒስ ክሊኒክ አመሩ። ዶውግ ሙሉ ጉልበቱን ለዚህ በሎስ አንጀለስ
ቬነስ ውስጥ ሊከፍቱት ባሰቡት የበጎ ፈቃድ ክሊኒክ ያለመሰሰት እውቀቱንና
ጉልበቱን ሲያውል እና የተለያዩ ዕቅዶችን ሲያወጣ ነበር፡፡ እዚህኛው
የከተማው ክፍል ውስጥ የሪል ስቴት ዋጋ እየጨመረ ስለመጣም አካባቢው
የቤት አልባ ሰዎች እና የአዕእምሮ በሽተኞች መናሃሪያ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ከእነዚህ ነዋሪዎች አብዛኛዎቹም ለብዙ ጊዜ የአደንዛዥ ዕፅ ተጠቃሚ እና
ሱሰኞች ናቸው። ዶውግ የክሊኒኩ ህንፃን በተቻለ አቅም በርካሽ ዋጋ ከገዛ
በኋላ ብዙዎቹን የአካባቢው አርቲስቶች፣ አርክቴክቶች እና ኮንትራክተሮች
በነፃ አገልግሎት ህንፃውን በደንብ አድርገው እንዲያድሱት አድርጎታል።
አሁን ላይ ሀዶን ነው ቦታውን በበላይነት የሚያስተዳድረው። ክሊኒኩ
ከጥቂት ወራት በፊት ቢከፈትም ሁልጊዜም ከክሊኒኩ እርዳታን የሚፈልጉ
ታካሚዎች ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ጀምረው ሰልፍ በመያዝ መጠበቃቸው የተለመደ ሆኗል።

ሀዶንም ክሊኒኩን እንድትጎበኝለት እና ምሳም አብረው እንዲበሉ ቀጠሮ፦
አስይዟት የነበረው ትሬይ ከመሞቱ በፊት ነበር። ስለዚህ ቀጠሮውን በማክበሯ ሁለቱም ተደስተው ነበር፡፡ ኒኪ ሀዶን ዶፍ መልካም እና የዋህ ሰው እንደሆነ ታውቃለች፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ ከሟቹ ባሏ ጋር ያላቸውን በደስታ የተሞላ ግንኙነት የሚያሳስባት ብቸኛው ሰው ነው ብላ ስለምታምን ነው በቀጥታ ከፖሊስ ጣቢያው ምሳ ለመብላት ወደ ተቀጣጠሩበት ቦታ የመጣችው፡፡ ማክሰኞ ማታ ላይ ስለተሞከረባት በመኪና ተገጭቶ የመገደል ሙከራን ልታካፍለው አልፈለገችም፡፡ ምክንያቱም አንዴ እሷ ይህን ጉዳይ አንስታ ለሀዶን ከነገረችው እሷን ለመጠበቅ እና ለመንከባከብ ሙከራዎችን እንደሚያደርግ በማሰብ ነው። ለዚህ ደግሞ ሀዶን ጊዜ እንደሌለው ከማንም በላይ ታውቃለች፤ በተለይ ደግሞ በቬነስ ክሊኒክ እና በሴዳርስ ሆስፒታል የሚያደርጋቸው ሰዎችን የማከሙ ነገር በጣም ብዙ ጊዜ እንዳይኖረው ነው ያደረገው። ስለዚህም አጠገቧ ሆኖ ሊጠብቃት እንደማይችል ስለምታውቅ ለእሱ ነገሩን በመንገር ማስጨነቅ አትፈልግም፡፡

ከሬስቶራንቱ ወጥተው ክሊኒኩ ወደሚገኝበት የስድስት ብሎክ ርቀት
ሲጓዙ ከበሉበት ሬስቶራንት አጠገብ ያሉት ውድ ውድ የድሮ ዕቃ መሸጫ እና ውድ ልብሶች መሸጫ ሱቆች 1920 ላይ ወደ ተሰሩት የጎጆ ኢንዱስትሪ ማምረቻ ህንፃነት እየተቀየሩ መጡ፡፡ በሰንሰለት የተዘጉ የህንፃ በሮች ሥር የበቀሉ አረሞች አሉ። ወደፊት እየተራመዱ ባሉበት ሰዓትም መንገዱ ዳር
ላይ የወዳደቁ የድሮ ጋሪዎች አሮጌ ጫማዎች፣ የተበላሹ ሳይክሎች
ወዳድቀው ይታያሉ። በዚህ አይነት ስድስት ብሎኮችን ተራምደው
እንደጨረሱ ኮርነር ላይ አንድ ሙሉውን ነጭ ቀለም የተቀባ በእንጨት
የተሰራ ክሊኒክ ጋ ደረሱ፡፡
👍1
የክሊኒኩ በር ላይም “የሮበርትስ እና ዶፎ ክሊኒክ
ሁላችሁም እንኳን በሰላም ወደ እዚህ መጣችሁ” የሚል ፅሁፍም ተፅፎበታል።

“ይሄው ደረስን” ብሎ ሀዶን ወደ ኒኪ ዞረ እና “እንዴት አገኘሺው? መቼስ በህይወት ቢኖር እና ቢመለከተው የሚወደው ይመስለኛል” አላት። ይህንን የሰማችው ኒኪም ስሜቷን ተቆጣጠረች እና “አዎን በእውነቱ ይወደው ነበር” አለችው፡፡

ወደ ህንፃው ውስጥ እንደገቡም ውጪ ያለው በተስፋ የተሞላ የነጭ ህንፃ ስሜት ልክ እንደ አረፋ ፊኛ ፈነዳባት። ወንድ እና ሴቶች አብዛኛዎቹ ወንዶች ናቸው፡፡ የክሊኒኩ ኮሪደር ላይ ቁጭ ብለው ወይንም ደግሞ አጎንብሰው ጉልበቶቻቸውን እንደያዙ አቀርቅረው በሚያሳዝን የስቃይ ስሜት ውስጥ ሆነው ይታያሉ፡፡ አንዳንዶቹ ታካሚዎች ከፕላስቲክ በተሰራው ከግድግዳው ጋር በተጣበቀ ወንበር ላይ ተቀምጠዋል። በሌሎቹ ሁለቱ በሽተኞች ወረፋ ይዘው በሚገኙት ክፍሎች ውስጥ የሚገኙ ሰዎች ደግሞ በተለያዩ የሱስ ደረጃዎች ውስጥ የሚገኙ ሱሰኞችና ህክምና እንዲደረግላቸው እየጮሁ ወይም እያጓሩ ነርሶቹን የሚያስቸግሩ ናቸው።

በእንደዚህ ሁኔታ ከሚያስቸግሩት ወንዶች መሀል ግን የኒኪ አይንን የሳቡ ሁለት ጎረምሶች ነበሩ። ፊታቸው እና ሰውነታቸው በጣም ከመክሳቱም በላይ የቆዳቸው ቀለም ሙሉ በሙሉ አረንጓዴ ስለሆነ በጣም ያስፈሩ ነበር።ከፊታቸው፣ ከእጃቸው እና ከክንዳቸው ላይም ልክ ከግድግዳ ላይ እየተፋቅ የሚወድቅ አይነት ቆዳ ነው ያላቸው:: የልጆቹ ፊት ላይም ፍፁም ተስፋ መቁረጥ የሚታይበት ሲሆን የህክምና እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ነበሩ።

“ሄሮይን ነው አይደል? ብላ ኒኪ በሀዶን ጆሮ ሹክ አለችው እና “ምስኪን
ሲያሳዝኑ። ደማቸው እኮ የተመረዘ ነው የሚመስሉት” አለችው፡፡

ህዶንም ለጥያቄዋ መልስ ከመስጠቱ በፊት ወደ ቢሮው አስገባት እና በሩን ዘግቶ እንድትቀመጥ አደረጋት፡፡

“ሄሮይን አይደለም” ብሎ ለኒኪ ነገራት፡፡ እናም “ግን ከእሱ ጋር ተመሳሳይነት ያለው የዴይስሞርፊን ዴሪቬቲቭ ነው። ስሙ ኮሮኮዳይል ወይም ደግሞ በሩስያኛ ክሮክዲል ይባላል፡፡ ይህንን ዕፅ ወደዚህ የሚያስገቡት ደግሞ ሩሲያውያን ናቸው።”

“ስያሜው የወጣለት የቆዳን ቀለም ልክ እንደ አዞ ቆዳ ቀለም
ስለሚለውጠው ነው?” ብላ ኒኪ ጥያቄዋን አቀረበች። ሀዶንም በአዎንታ ራሱን ነቅንቆ “በጣም በሚያሳቅቅ ሁኔታ ነው ተጠቃሚውን የሚጎዳው። ዶውግ
ስለዚህ የዕፅ አይነት ነግሮሽ አያውቅም?”

ኒኪም ራሷን በአሉታ ወዝውዛ “አይመስለኝም” አለችው፡፡

“ይሄ አደንዛዥ ዕፅ አሁን ላይ ሎስ አንጀለስ ውስጥ አዲስ አደንዛዥ ዕፅ
ነው።” ብሎ ይበልጥ እያብራራላት “ሩስያውያንና ሜክሲካውያን እዚህ
ከሚገኘው የአደንዛዥ ዕፅ ቢዝነስ ገፍተው ሊያስወጧቸው ይፈልጋሉ።
ወይም ደግሞ ከሩስያውያን ጋር በከፍተኛ ፉክክር ውስጥ ይገኛሉ። በሁለቱ
አደንዛዥ ዕፅ አቅራቢዎች ፉክክር የተነሳ ግን በጣም እየተጎዱ ያሉት እንደነዚህ ያሉት ልጆች ናቸው፡፡ እናም ክሮክ የተባለው አደንዛዥ ዕፅ አሁን ላይ የአደንዛዥ ዕፅ አቅራቢዎች ዋነኛው ትውልዱን መግደያ መሳሪያቸው
ነው።”

“ችግር የሚሆነው ደግሞ ለምን መሰለሽ? አደንዛዥ ዕፁ በጣም በቀላሉ
በቤት ውስጥ መዘጋጀት የሚችል መሆኑ ነው፡፡ ይሄ ማለት ደግሞ እነዚህ
አደንዛዥ ዕፆች ውስጥ የተለያዩ ብዙ ነገሮች ይገኛሉ ማለት ነው። የግድግዳ
ቀለሞች ሀይድሮክሎሪክ አሲድ እና ሌሎችም ንጥረ ነገሮች ይገኙበታል። ይህ
አደንዛዥ ዕፅ ሩስያ ውስጥ ለረዥም ጊዜ ሲጠቀሙበት ነበር። አሁን ላይ
ደግሞ እዚህ እንደ አዲስ ሥር እየያዘላቸው ነው::”

“እንደዚህ አይነት በዕፅ የተጎዱ ብዙ ህፃናት አይተህ ታውቃለህ?” ኒኪ አረንጓዴ ቆዳ ያላቸው ጎረምሳዎች ፊት ከውስጧ ስለቀረባት ጥያቄን አቀረበችለት።

“አዎን በየሳምንቱ እንደዚህ አይነት ልጆች ይገጥሙናል” ብሎ ሀዶን መለሰላት እና በማስከተልም “ያው ቅድም እንደነገርኩሽ ነገሩ የንግድ ጦርነት ነው፡፡ ሩሲያውያኖቹ ይህንን በውስጡ ብዙ ንጥረ ነገር ያለውን አደንዛዥ እፅን ለተጠቃሚዎች ያቀርባሉ፡፡ አሁን ላይ ደግሞ ሜክሲካውያኑ ምርጥ
ንፁህ እና ከሩሲያኖች የተሻለ ክሮክን በማቅረብ የንግድ ፉክክሩን እያጦዙት
ነው፡፡ በእርግጥም ሚክሲካውያኑ የሚያቀርቡት ምርት ከሩስያኖቹ ጋር
ሲነፃፀር ዋጋው ውድ ቢሆንም አሁንም ቢሆን በቀላሉ የሚገኝ እና ርካሽ
ነው።”

“የማግዝህ ነገር ይኖራልን?” ብላ ኒኪ በቅንነት ጥያቄዋን አቀረበች::
ሀዶንም ለእሱ ሀሳብ የእርዳታ እጇን ለመዘርጋት በቅንነት ስለጠየቀችው
ልቡ ተነካ እና “አመሰግናለሁ የኔ ውድ” ብሎ እጇን ጨምቆ ያዘው እና በእውነት ጥያቄሽን ስላቀረብሽልኝ ደስ ብሎኛል። ግን አንቺ በጣም በብዙ ነገሮች ውስጥ ያለፍሽ ስለሆነ እና መረጋጋትሽንም የሚጠበቅ በመሆኑ አሁን ላይ እገዛሽ አያስፈልገኝም::” አላት።

“ዶውግ አንቺን ብዙ ጊዜ ሊንከባከብሽ ይፈልግ ነበር። እኔም ብሆን አንቺን ልንከባከብሽ ብችል ደስ ይለኛል፡፡ በተለይ ደግሞ አሁን ላይ ባለሽበት ስሜት ውስጥ በመሆንሽ ትሬይ እና ፍላንገን የተባለችው ታካሚሽ ላይ በደረሱት ነገሮች ጥሩ ስሜት ውስጥ እንዳልሆንሽ አውቃለሁ። በነገራችን ላይ ፖሊሶች በጉዳዩ (በወንጀሉ) ዙሪያ ያገኙት አዲስ ነገር አለ?” ብሎ ጠየቃት፡፡ ኒኪም “የለም” ብላ ድምጿ በቁጣ እንደተሞላ መለሰችለት፡፡ ፊቷ ላይ የነበረው የደስታ ስሜትም ጠፋ። ምናልባትም ባልጠበቀችው ጊዜ የሟች
ባሏ ሥም በመጠቀሱ ሊሆን ይችላል ፊቷ ሊኮሳተር እና የተረበሽ ስሜት
ሊታይበት የቻለው ሲል አሰበ፡፡

“ይቅርታ” ብሎ ሀዶን ተናገረ እና በመቀጠልም “አንቺን ለማበሳጨት
አስቤ አልነበረም” አላት፡፡

“ኧረ አላበሳጨኸኝም” ኒኪ ሊፈስ የቀረበውን እምባዋን እንዳይወርድ
እየታገለች “አሁን እኔ በጣም ደህና ነኝ” ብላ መለሰችለት።

ከዚያ በኋላም ክሊኒኩን በሚጎበኙበት ጊዜ ላይ ያገኘቻቸው የክሊኒኩ
ሰራተኞች እያቀፏት እና እየጨበጧት በባሏ ዶውግ ሞት የተሰማቸውን
የሀዘን ስሜት ይገልፁላት ጀመር፡፡ ለሰላሳ ደቂቃ ያህል ክሊኒኩን ጎብኝታ ከጨረሰች በኋላ ስትሰናበተው ኒክን አቀፈችው::

“ቅድም ስለሆንኩት ነገር ይቅርታ” አለች እና “ዶውግ እኔን ይንከባከበኝ ስለነበረው ነገር ስታወራኝ እኔን ስለደበቀኝ ነገሮች ማሰብ በመጀመሬ የተነሳ ነው እንደዚያ የሆንኩብህ፡፡ ሁሉንም ሚስጥሮቹን። ያው ለእኔ በጣም አስቸጋሪ ጊዜ ነበር ታውቃለህ መቼስ?” አለችው። “ይገባኛል” አላት እና ደፎ እቅፍ አድርጎ ወደ እራሱ አስጠጋት፡፡ በመቀጠልም

“እኔን ይቅርታ ማለት አይጠበቅብሽም፡፡ በቃ ለራስሽ ብቻ ትኩረት ለመስጠት ሞክሪ ኒኪ። ወደ ኋላ ሳይሆን የወደፊቱን ህይወትሽን ተመልከቺ።” አላት።

ኒኪ ፈገግ ብላ “እሺ ዶ/ር ዶፎ እስቲ እንዳልከኝ ለማድረግ እሞክራለሁ”
ተሰናብታው መኪናዋን አስነስታ ስትወጣ ሀዶን የብሎኩ ጥግ እስከምትደርስ እና ታጥፋ ከአይኑ እስከምትሰወር ድረስ ቆሞ ይመለከታት ጀመር። በቆመበትም ጠንክራ ያለፈውን ህይወቷን እንድትረሳ እና ወደፊት እንድትቀጥል ፀሎቱን አደረሰ። ምክንያቱም ለሁለቱም ከዚያ የተሻለ ነገር የለም።

ዶክተር ሀዶን ዶፎ አንድ አንድ በሮች አንድ ጊዜ ከተዘጉ በኋላ
እንደማይከፈቱ ከማንም በተሻለ ያውቃል። ሟቹ ጓደኛው ዶውግ ሮበርትስ ደግሞ እሷ ከምታውቀው በላይ
ይጠብቃት እና ይንከባከባት ነበር።

ይቀጥላል
አትሮኖስ pinned «#የፍቅር_ሰመመን ፡ ፡ #ክፍል_ሀያ ፡ ፡ #ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን ፡ ፡ #ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው ...ለምንድነው እሷ የሌሎችን ፈጠራ የምትነግረን?” ብሎ ጉድማን እጆቹን እያወናጨፈ “ ለምን?” ብሎ ጠየቀው፡፡ ጆንሰንም ትከሻውን ሰብቆ “ምናልባት ትኩረት ለማግኘት ፈልጋ!” እኮ ያንተን ትኩረት? ላስቀይምህ አይደለም ኒኪ፤ ግን እሷ አንተ ላይ ምንም አይነት ፍላጎት የላትም” “አላውቅም ሉው። ምናልባት…»
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሀያ_አምስት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

....ሶስና ነበረች የመለመለቻት…አንድ በአንድ ይታወሳታል... ጓደኛዋ ሶስና ነበረች የመለመለቻት፡፡

ርብቃ ሶስናን የምታውቃት በዩኒቨርስቲ ዓመቶቿ ነው፡፡ ሁለቱም የቋንቋ ተማሪዎች ነበሩ፡፡ ከትምህርት ዓለም ተሰናብተው ወደ ሥራ ዓለም ሲሸጋገሩ ሶስና በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ርብቃ ደግሞ በማስታወቂያ ሚኒስቴር ሥራ ያዙ፡፡

የሥራ ቦታቸው መለያየት ሊለያያቸው የሚችል ቢሆንም አልተራራቁም፡፡ ቢያንስ በሣምንት አንዴ እየተገናኙ አብረው ጊዜያቸውን ያሳልፉ ነበር፡፡ በመጨረሻም የለያያቸው ሶስና በአንደኛ ፀሃፊ የሥራ መደብ ካይሮ ወደሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ መሄዷ ነበር፡፡

ባለፈው ዓመት መጨረሻ ገደማ ላይ ነበር፡፡ ከሥራ ሰዓት በኋላ ዘወትር እንደሚያደርጉት ቀጠሮ ተሰጣጥተው ተገናኝተው ሲጫወቱ አመሹ፡፡ ወደ አሥራ ሁለት ሰዓት ላይ ሶስና ድንገት ተነስታ ቀጠሮ እንዳላት ስትነግራት ርብቃ አዲስ ነገር ሆነባት።

“በዚህ ሰዓት?” አለች መምሽቱን ተመልክታ፡፡
አዎ ርብቅዬ... ማታ ማታ ነው የምንገናኘው።”
“ማነው ባክሽ?” አለች ርብቃ እየተሽኮረመመች፡፡

“ኦ! ወንድ መስሎሽ ነው እንዴ አይደለም ጓደኞቼ ናቸው፡፡”
“እኔ የማላውቃቸው ጓደኞች! ሂ! ሂ! ሂ!” ርብቃ ሳቀች ጓደኛዋ የደበቀቻት ምሥጢር እንዳለ በማመን፡፡

“ርብቃ ሙች እንዳስብሽው አይደለም፡፡ ምን መሰለሽ በእርግጥ አታውቂያቸውም፡፡ እኔም ቅርብ ጊዜ ነው የተዋወቅኋቸው.. እና አልፎ አልፎ ተገናኝተን በተለያዩ አርዕስቶች ላይ እንነጋገራለን፡፡”

“ምን ልትፈጥሩ?” “ አለች ርብቃ ጓደኛዋ የምትለው መላቅጡ ሲጠፋት፡፡

“የተሻለ ዓለም!” አለች ሶስና ጓደኛዋ ትኩር ብላ እየተመለከተቻት ምን መሰለሽ .. ” አለች የርብቃን መደናገር ስታይ፡፡ “በአንድ ርዕስ ላይ ስትከራከሪ የተለያዩ ሃሳቦችን ታገኝያለሽ፡፡ ጭንቅላትሽ ይሰፋል አስተሳሰብሽም ይዳብራል፡፡”

“እና ለመከራከር ተቀጣጥራችሁ ትገናኛላችሁ ማለት ነው?”

“አዎ አንድ ርዕስ እንመርጥና እንዘጋጅበታለን፡፡ ለምሳሌ ስነጽሁፍ …ወይ…ኋላቀርነት ወይ አፍሪካ በቃ እንድ ርዕስ ከዛ በርዕሱ ላይ እያንዳንዳችን እንዘጋጅና ተገናኝተን የሰበሰብነውን
እንለዋወጣለን! እንከራከራለን፡፡” .

“ጥሩ ነው ሃሳቡ፡፡” አለች ርብቃ ቦርሳዋን እያነሳች:: “በይ ከሄድሽ ቶሎ እንሂድ፡፡ እንዳይመሽብሽ፡፡”

“ለምን አብረን አንሄድም?”
“የት?!” አለች ርብቃ ጓደኛዋ ላይ አፍጥጣ፡፡
“አሁን ያልኩሽ ቦታ ነዋ::”
“አበድሽ እንዴ? ደግሞ እኔ ምንድነኝ? አንቺኮ ጓደኞችሽ ስለሆነ…”
“አይደለም. አይደለም:: ባይገርምሽ አብዛኛዎቻችን የተዋወቅነው
እዛው ነው:: እየሽ እያንዳንዱ አባል ብስለት አለው የሚለውን ሰው መጋበዝ
ይችላል፡፡እና ተጋባዥ እንድ ፕሮግራም ይካፈልና ከጣመው አባል ይሆናል፡፡”

“ሌላ ጊዜ።” አለች ርብቃ የጓደኛዋን ክንድ ይዛ ከነበሩበት ቡና ቤት እየወጡ፡፡

ለምን? ነይና እይው፡፡ ምንም መናገር አያስፈልግሽም፡፡ ዝም ብለሽ ተቀምጠሽ እኛ ስንወያይ ታዳምጫለሽ፡፡ እንዳልኩሽ ፕሮግራሙ የሚጠቅምሽ ከመሰለሽ… እያየሽ ትቀጥያለሽ፡፡ ማን ያውቃል ብዙ ነገር ታስተምሪን ይሆናል፡፡ ጋዜጠኛ መሆንሽን ሲያውቁማ ወጥረው ነው የሚይዙሽ፡፡” ሶስና ገፋፋቻት፡፡

“ጋዜጠኛ ለፍላፊ ነው ለማለት ነው ብሽቅ!” አለች ርብቃ ጓደኛዋ
የወትሮውን ብሽሽቅ የጀመረች መስሏት፡፡
“አይደለም... አየሽ ጋዜጠኞች በተለያዩ አርዕስቶች ላይ ስለምትስሩ ከተራው ሰው የተሻለና ሰፋ ያለ እውቀት ይኖራችኋል፡፡ ይህ ደግሞ የሚያከራክር አይደለም፡፡ የኛ ጋዜጠኞች ደግሞ ዋዛዎች አይደላችሁም፡፡

“እ…እ”
“ሙች ሙች ከምሬ ነው:: ሌላውን ብንተወው እንኳን… ለየግላችሁ ያላችሁ ዕውቀት የሚናቅ አይመስለኝም:: ብቻ እስቲ ነይና እይው።”

“እረ በናትሽ ሳይጠሩኝ ሰተት ብዬ ቤታቸው ስሄድ ምን ይለኛል?

“በደስታ የሚፈነድቁት ርብቃ ሙች! አዲስ ሰው በመጣ ጊዜ ምን ያህል እንደምንደሰት ብታውቂ… አዲስ አስተያየት፤ አዲስ አመለካከት ማለት ነው!”

“ግን ታመሹ እንደሆነ?”
“ምንም ችግር የለም። መኪና የሚይዙ ስላሉ ሁላችንን በየቤታችን የሚጥሉን እነሱ ናቸው፡፡ እሱ አያሳስብሽ…እሺ በቃ እንሂድ… እሺ?” ውጥር አድርጋ ያዘቻት፡፡

“ግን… እንጄ.…” እያለች ነበር ርብቃ ለመሄድ የተስማማችው::

ታክሲ ተሳፍረው በንፋስ ስልክ መስመር ወደ ጎተራ አቅጣጫ አመሩ፡፡ መሃል ላይ ሶስና “እዚህጋ ይበቃናል፡፡” ብላ ታክሲውን አስቁማ ሲወርዱ ሊጨልም ዳድቶት ነበር፡፡ አንድ ሰዓት ከአሥር፡፡

“አርፍደናል፤ከአንድ ሰዓት በፊት መገኘት ነበረብን፡፡” አለች ሶስና ከዋናው መንገድ በስተግራ ተገንጥሎ ሽቅብ ወደሚወጣ መንገድ እያመራች።
ጎን ለጎን እየተራመዱ በዝምታ ቀጠሉ። ከአንድ ግራጫ ቀለም ከተቀባ
የብረት በር አጠገብ ሲደርሱ ሶስና ጠጋ ብላ መጥሪያውን ተጫነችው።

አራት ማዕዘን ቅርፅ ያላት ትንሽ የስርቆሽ በር ተከፈተችና አንድ ሰው አጮልቆ ተመለከታቸው። ሶስና ምንም ሳትናገር ጠጋ ብላ ፊቷን አሳየችው፡፡ የስርቆሽ በር ተዘጋችና ዋናው የብረት በር ተከፈተላቸው፡፡ ገቡ፡፡

ርብቃ ከማታውቀው ቤት ሳትጠራ በመምጣቷ እፍረት ቢሰማትም
ውስጥ ገብታ ጉዷን እስክታየው ቸኮለች። ከፊት ለፊት ያለው ቤት ትልቅ ሳይሆን ቀልብጭ ብሎ በጥሩ ሁኔታ የተያዘ ይመስላል፡፡ ምናልባት በቅርብ
ጊዜ የተሰራ ስለሆነም ሊሆን ይችላል፡፡ ከፊት ለፊት የሚታዩት ሁለት
መስኮቶች ተዘግተዋል፤በግቢው ውስጥ ከጥግ እስከጥግ እንደምንጣፍ
የተነጠፈው አስፋልት መሐል የሚታይ የአትክልት ዘር የለም፡፡ ቤቱ
ሕይወት ያለበት አይመስልም፡፡
የገዛ ቤቷ እንደሆነ ሁሉ ሶስና ነይ፡፡ አይዞሽ አትፍሪ” እያለች የዋናውን ቤት የፊት በር ከፍታ ገቡ፡፡ ከውስጥ የተቀበሳቸው ጨለማ ነበር፡፡
በጠባቧ መተላለፈያ ውስጥ ባለው ደብዘዝ ያለ ብርሃን ሦስት የተዘጉ በሮች
ይታያሉ፡፡ ስልክ የተቀመጠበት ትንሽ ጠረጴዛና ወንበር ጥግ ይዘዋል፡፡
በተረፈ ምንም የለም:: ድንገት የታፈነ የሚመስል ድምፅ በስተቀኝ በኩል
ካለው በር ጀርባ መጣ፡፡ ሰዎች የሚነጋገሩ ይመስላል በለሆሳስ፡፡

ነይ እንጅ…” አለች ሶስና በስተቀኝ ወዳለው በር እያመራች፡፡ ርብቃ
ከተል አለቻት፡፡

ከውስጥ የተቀበላቸው ክፍል ከመተላለፊያው የተሻለ ብርሃን ያለበት
ቢሆንም እዚያም ያለው ጨለማ ለአይን የሚከብድ ነበር፡፡ እራቅ ካለ ማዕዘን
የቆመው ባለ ረጅም ቋሚ መብራት ድብዝዝ ያለ ብርሃን ይተፋል፡፡ ከቋሚ
መብራቱ ቀይ ጨርቅ የሚፈሰው ብርሃን ቤቱን ፍም አስመስሎታል፡፡

“ይቅርታ ስላረፈድን፡፡ አንደምን ዋላችሁ።” አለች ሶስና በደፈናው፡፡

በሳሎኑ ክፍሉ ውስጥ ሰዎች ተቀምጠዋል፡፡ ወዲያ ማዶ የተዳፈነው
ቀይ ብርሃን አጠቃላይ ቁመናቸውን እንጅ ገፅታቸውን ጥርት አድርጎ አያሳይም።

“ዛሬ አዲስ እንግዳ ይዤ ነው የመጣሁት።” አለች ሶስና የርብቃን
እጅ ይዛ ወደ ሳሎኑ እየተጠጋች፡፡
ማናቸውም ድምፅ አላሰሙም፡፡ በተቀመጡበት “ጭንቅላታቸውን
እያነቃነቁ ስምምነታቸውን ሲገልፁ ርብቃ በጨለማ ውስጥ ሸንጎ የተቀመጡ
አማልክት መሰሏት።
ሶስና ከማናቸውም ጋር አላስተዋወቀቻትም::የርብቃን ስም አልተ
ናገረችም፡፡ አንድ ፎቴ ላይ እንድትቀመጥ ካመለከተቻት በኋላ ከወደጥግ ካለ
ጠረጴዛ ላይ ወደ ተቀመጠች አነስተኛ ማቀዝቀዣ ሄዳ ከፈተቻት፡፡ ለአንድ
አፍታ ከማቀዝቀዣዋ ውስጥ የወጣው ብርሃን በሳሉን ክፍል ውስጥ ሲናኝ
ርብቃ ከፊት ለፊቷ የተቀመጡትን ሦስት ሰዎች ተመለከተቻቸው… ሁለቱ
ወንዶች ሲሆኑ በስተቀኝ ዳር ያለችው ሴት ነች… በስተግራዋ
የተቀመጡትን ሰዎች ግን ለመመልከት አልቻለችም፡፡ የማቀዝቀዣዋ ብርሃን ከጀርባቸው
ነበር፡፡

ወዲያው ሶስና ማቀዝቀዣዋን ስትዘጋ ክፍሉ በቀድሞው ጨለማ ውስጥ ሰመጠ፡፡ ሶስና ከማቀዝቀዣዋ ውስጥ ያወጣቻቸውን ሁለት የኮካኮላ
ጠርሙሶች ይዛ ከጠረጴዛው ላይ ከተደረደሩት ብርጭቆዎች መሃል ሁለቱን
አንስታ ይዛ ተመለሰችና ርብቃ ጎን ተቀመጠች፡፡ጠርሙሶቹን ከፍታ ከቀዳች
በኋላ ቀና አለች፡፡

“ይቅርታ…አቋረጥናችሁ…?”

ችግር የለም። ገና ስንጀምር ነው የደረሳችሁት።” አለ ፊት ለፊት
የተቀመጠው ዕው፡፡ ድምፁ ረጋ ለዘብ ያለ ነው፡፡ ወዲያው በስተግራ
ወደተቀመጠው ሰው ዞር አለና “እሺ ቀጥል፡፡” አለ፡፡

“አዎ… እና …እንዳልኩት ሁላችንም ባርያዎች ነን…” አለ በስተግራ
የተቀመጠው ሰው በዙሪያው የተኮለኮሉትን ሁሉ በተራ እየተመለከተ
“ባርያ!” አለ ድጋሚ ጮክ ብሎ፡፡ “የካሊፎርኒያው ነጭ የስነልቦና ሊቅ
አርዘር ጆንሰኝ እንዳለው በዝቅተኛ የአእምሮ የዕድገት ደረጃ ላይ በሰውና
በዝንጀሮ መሃል የምንገኝ ፍጡሮች ነን እኛ አፍሪካውያን፡፡ ይህንን ባንቀበል
ደግሞ ተጨማሪ ድንቁርና ይሆንብናል፡፡ ማለቴ ባርነታችንን፡፡ እዚህ ላይ
ባርያ ስል ማስተዋል የጎደለው ለራሱ ሊቆም የማይችል አሳፋሪ ዝርክርክ
ተቀጥላ ፍጡር ማለቴ እንጅ ምናልባት አንዳንዶቻችሁ እንደምታስቡት
ጥቁርና ለንቦጫም ማለቴ አይደለም፡፡ በፍጹም! እስቲ አዲስ የመጣችውን
ልጅ አንድ እንቆቅልሽ ልጠይቃት…” አለ ሰውየው ድንገት ወደ ርብቃ ፊቱን
መልሶ፡፡ “አስቢው! ይታይሽ የገዛ ከርሱን ሊሞላበት ከውጭ የሚጠብቅ ፡
የገዛ ገላውን ሊሸፍንበት ከውጭ የሚጠብቅ፤ በባዕድ ዳንኪራ እየረገጠ እርስ በርሱ የሚናከስ ዝንጀሮ ማነው? ንገሪኝ አለዛ አገር ስጪኝ!” ጮኹባት።

ርብቃ ተማታባት።

“አለቀ!” አለ ኣለመናገሯ ስምምነት እንደሆነ ሁሉ። “አፍሪካዊ ነው
ባርያ!”

ለአንድ አፍታ በክፍሉ ውስጥ ፀጥታ ነገሠ።

“እንቆቅልሽ ለእኔ ቀርቦ ቢሆን ኖሮ 'አፍሪካዊ' ሳይሆን ኋላቀር ህዝብ እለው ነበር መልሱን፡፡” አለ በስተግራ ከተቀመጠት ሰዎች ሁለተኛው፡፡ “በዓለማችን ኋላቀር የሆንን ህዝቦች ደግሞ አፍሪካውያን ብቻ ነን ለማለት ያስቸግራል፡፡”

ደቂቃዎች እየተሽቀዳደሙ በነጎዱ ቁጥር ክርክሩ እየጦፈ የተናጋሪዎች እልህ እየጋመ ሲመጣ ርብቃ በዝምታ አንድም ሳይቀራት ተከታተለቻቸው፡፡ ዝግጅቱ ኣልቆ ሲበተኑ ሶስና አብረው እንዲያድሩ ስለጠየቀቻት ከተሰብሳቢዎቹ መሃል አንደኛው ሁለቱንም በመኪናው ሶስና ቤት ድረስ አድርሷቸው ተሰናብቷቸው ተመለሰ፡፡

ሶስና የቤቷን በር ከፍታ እስኪገቡ አልተነጋገሩም ነበር፡፡

“ሶስና...ግን ያ ሰውዬኮ እውነቱን ነው፡፡ መጀመሪያ ሲናገር በጣም ነበር ያበሸቀኝ::ማለቴ… ባርያ ነን ሲል፡፡ ግን በኋላ ባስበው የጨፈነኝ አጉል ኩራት መሆኑ ገባኝ፡፡” አለች ርብቃ ወደ ውስጥ እንደገቡ፡፡

“እንዴት?” አለቻት ሶስና ትኩር ብላ እያጠናቻት፡፡

“አስቢው እስቲ፡፡ እውነቱንኮ ነው፡፡ ባርያ ማለት ልዩ ፍጠር ማለት አይደለም:: የራሱን መብት ማስጠበቅ የማይችል ማለት ነው፡፡ እስቲ የትኛው አፍሪካዊ ኣገር ነው በሁለት እግሮቼ ቆሜአለሁ ብሎ አፉን ሞልቶ የሚናገር? ታዲያ በሁለት እግሩ መቆም ያልቻለ ህፃን ሲሰጡት ከመቀበል ሲከለክሉት ከመነጫነጭ አልፎ በየት አገር ነው መብቱን የሚያስጠብቅ? አንቺ እማምላክን ዛሬም ባርያዎች ነን!” የተናገረችው ለራሷ የቀፈፋት ይመስል ርብቃ እጇን አፏ ላይ ጫነችው፡፡

ከዛን ቀን ጀምሮ በየሳምንቱ ሁለት ሁለት ቀን እዚያው ቤት እየተመላለሰች ለአራት ወራት ዝግጅቱን ስትካፈል ቆየች። መረቡ እንደ ሸረሪት ድር ከተበተባት ኣጥማጆቿ እንዳቀዱት አፍሪካዊነቷ ነፍስ ዘርቶ
እንደ ሽል ሆዷ ውስጥ መገለባበጥና መራገጥ ከጀመረ ሰኋላ ነበር ሁኔታው
የተገለፀላት፡፡

ለአራት ወራት እብረዋት ተቀምጠው ሲከራከሩና ሲፋተጉ የነበሩ ሁሉ ይሰሩት የነበረው ቲያትር መሆኑን የተገነዘበችው እጅግ ዘግይታ ነበር፡፡ ሁሉም የያዙት አቋም አንድ ነበር፡፡ወክለው የሚከራከሩት ወግነው የሚፋተጉት ግን የእሷኑ ህሊና ግራና ቀኝ ነበር፡፡ ሳታውቀው ሳትገነዘበው
መረባቸው ውስጥ ገባች፡፡ አይኖቿ በሩላት፡፡ እሷም እንደ ኣጥማጆቿ ሌሉች
አይናቸው ያልበራላቸውና ኣይናቸው የሞጨሞጩ እስቀያሚዎች ሲመጡ
“ባርያ! ባርያዎች ነን!” እያለች እልህ ዘራች፤ቁጭት አበቀለች፤አፍሪካዊነት አጨደች፣ቆንጆዎች አመረተች።

ስብሰባውን መካፈል በጀመረች በስባተኛው ወር ነበር በህቡዕ
ድርጅቱ ውስጥ በአፍሪካዊነቷ ልታገለግል በመሉ ልብ ቃል የገባችው::
መጀመሪያ ቀን በተለበለበችባት ጨለማ ክፍል ወስጥ በክፍሉ ውስጥ የእሷው ብጤ አዲስ ተጠማቂዎች ተሰብስበዋል
ስምንት፡፡ ሌሎች የማታውቃቸው እንግዶችም በሥነሥርዓቱ ላይ ተገኝተው
ነበር፡፡ ክፍሉ ውስጥ በአጠቃላይ ያለው ሰው ሃያ ይደርሳል፡፡ አብዛኞቹ በእርሷ የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ሲሆኑ መሃል ፎቴው ላይ ቦታ የተለቀቀላቸው አራት ሰዎች ግን በዕድሜ የገፉ ነበሩ፡፡
ሰዎቹ የተገኙት ዝግጅቱን ለመምራትና አዲስ አባላቱን ለመቀበል ነበር፡፡ ርብቃ በደብዛዛዋ ብርሃን ውስጥ ተመለከተቻቸው፡፡ ሦስቱን ሰዎች
በፍጹም አታውቃቸውም…. በግራ በኩል ጥግ ላይ የተቀመጡትን አንደኛውን
ሰው ግን ለይታ ስማቸውን ባትጠራም ከዚህ በፊት መልካቸውን ማየቷ ትዝ
ያላታል፡፡ ቢሆንም የት እንደሆነ ልታስታውስ እልቻለችም::

ዝግጅቱ እንደተጀመረ ከአራቱ አዛውንት አንደኛው ንግግር አደረጉ፡፡

“ከሰላሳ ዓመታት በፊት በ1963 አዲስ አበባ ላይ ከየአቅጣጫው የተሰበሰበው የጥቂት ነፃ አፍሪካ አገሮች መሪዎች ስብሰባ ላይ ተገኝቼ ነበር፡፡ያኔ እኔም እንደ እናንተ ገና ትኩስ ጎልማሳ ነበርኩ::” አሉ ከተቀሩት ሦስት አዛውንት በዕድሜ ላቅ ያሉ የሚመስሉት የመሃለኛው:: ደብዛዛው ቀይ ብርሃን በትልምና በደረጃ በተከፋፈለው ፊታቸው ላይ ሲያርፍ የቀለጠ ነሃስ አስመስሏቸዋል፡፡ ቀዩ ብርሃን ሊነካው ዝገት የሚመስለውን ሽበት የበዛበት ፀጉራቸውን ..እንደ ጧፍ የሚንቀለቀለውን አይናቸውን በእምቢተኝነት ቀጥና ቀና ያለ ትከሻቸውን ስትመለከት ርብቃ ሃውልት መስሏት፤ቅርስ፡፡

“ያኔ…” ቀጠሉ ፊታቸው የሃዘን ፈገግታ ለብሶ፡፡“ያኔ በእያንዳንዳችን ልብ ውስጥ የተስፋ ጸዳል ይንቀለቀል ነበር…ያኔ …ጠንካራ አፍሪካን ገንብተን ከሌላው የሰው ዘር ጋር ትከሻ ለትከሻ ልንቆም እርግጠኞች ነበርን፡፡ ከሰላሳ
ዓመታት በፊት…ድሮ፡፡ በስብሰባው ላይ የአፍሪካ አባት ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ
የተናገሩት ምን ጊዜም ከአእምሮዬ አይጠፋም፡፡ አንድነታችን ከጊዜ ጋር
የምንቀዳጀው ነው፡፡ በቀን ተቀን በምናደርገው እንቅስቃሴ ጠንካራ
መሠረት ከጣልን ግንበኛውና መሣሪያው ከሰጠ… ጠንካራ ቤት እንገነባለን፡፡ ነበር ያሉት፡፡ ሰላሳ አመታት አለፉ። ያ ቤት አሁንም አልቆመም።ይብሱን የተጣለው መሠረት ይሰነጣጠቅ ጀመር! የግንበኛው አላዋቂነት ይሆን ወይስ ግንበኞች በዙ? ልባም ሠራተኛ ጠፋ? ወይስ በጣሽ ቀጣዩ ሂያጅ መጪው ፈላጭ ቆራጩ በረከተ? ”

የክፍሉ ፀጥታ ከመቃብር ከበደ።....


💫ይቀጥላል💫
👍2
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_ሀያ_አንድ


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው


....ሎው ጉድማን ስታር ተብሎ ከሚጠራው የሎስ አንጀለስ መንገድ ላይ መኪናውን ሲያስገባ ፀሐይ መጥለቅ ጀምራ ነበር። የሴንቸሪ ሲቲ ትልቅ ፎቅ
ደግሞ በሎስ አንጀለስ ሐምራዊ ብርቱካናማ የምሽት ፀሐይ የሆነ ህልም
ውስጥ የሚገኝ ፎቅ መስሎ ቆሟል።
በመንገዱ ዳር እና ዳር የሚገኙት
የዘንባባ ዛፎችም በሞቃታማው ንፋስ ልክ እንደሰከረ ሰው ይወዛወዛሉ።

የፖሊስ ባጁን እንደያዘም የህንፃው እንግዳ ተቀባይ ዴስክ አጠገብ
በመድረስ “መርማሪ ፖሊስ ሉው ጉድማን የግድያ ወንጀል ምርመራ ፖሊስ
ነኝ፡፡ ክፍል ቁጥር 706 ን ለማየት ነው የመጣሁት እና ቁልፉን ትሰጪኝ”
አላት ላላቲኖዋ እንግዳ ተቀባይ ፈገግ እያለ፡፡ ልክ እንደሁልጊዜው የፍርድ
ቤት ማዘዣ ወረቀት ሳይዝ እንደሚያደርገው ማለት ነው፡፡

ልጅቷም የአፀፋ ፈገግታዋን ለግሳው እና በውስጧም ኮሌምቢያ ውስጥ ከምታውቃቸው ፖሊሶች የተሻለ መልካም ፀባይ እንዳለው እያሰበችም “ አለኝ፡፡ ግን አያስፈልግህም፡፡ ዶክተር ሮበርትስ ቢሮዋ ከገባች አንድ ሰዓት አልፏታል። አሁንም ቢሮዋ ውስጥ ትገኛለች፡፡ በግራ በኩል ያለውን አሳንስር መጠቀም ትችላለህ አለችው።

"አመሰግናለሁ” አላት መብሸቁን ለመደበቅ ፈገግ እያለ፡ ጉድማን የኒኪ
ቢሮ ውስጥ ብቻውን በመግባት ቢሮዋን መበርበር ነበር የፈለገው፡፡ በዚህ
ሰዓት ምን ትሰራለች? ብሎ ራሱን ጠየቀ፡፡ ግን ቢሮዋ ውስጥ እሷ መኖሯ ጥሩ ነው ብሎም አሰበ፡፡ ምክንያቱም ቀን ላይ ባልደረባው ጆንሰን እሷን ስላበሸቃት ብዙ ልትነግራቸው የምትፈልጋቸውን ነገሮች መናገር ትታ ነበር::ምናልባት አሁን እሱ ብቻውን ስለሆነ ይበልጥ ግልፅ ሆና ልታወራኝ ትችላለች ብሎ አሰበ እና ተረጋጋ።

በአሳንሰሩ ሰባተኛው ፎቅ ድረስ ወጣና በኮሪደሩ ላይ እየተራመደ የዶክተር ኒኪ ሮበርትስ ቢሮ ጋ ሲደርስ ቆመ፡፡ በሩ ገርበብ ብሎ ስለተከፈተም ወደ ውስጥ መሰስ ብሎ ገባ፡፡ ኒኪ ጀርባዋን ሰጥታ በወረቀት መክተፊያው ማሽን ውስጥ ወረቀቶችን እያስገባች ወረቀቶችን እየከተፈች ነበር፡፡ እግሯ ሥር ካስቀመጠችው ካርቶን ውስጥ ዶክመንቶችን እያነሳች ወደ ማሽኑ እየከተተች እና እየከተፈች ልትጨርስ ስትል

“እንዴት ነሽ?” የሚል ሰላምታን ስጣት፡፡

ኒኪም ድምፁን ስትሰማ በከፍተኛ ድንጋጤ ቀለሙ የተለወጠውን ፊቷን
ወደ እሱ በማዞር ፍርሃት በተሞላ አይን ተመለከተችው፡፡

“በእግዚአብሔር! በፍርሃት ነፍሴ ልትወጣ ነበር!” አለችው፡፡

“ይቅርታ” አላት እና እጇ ላይ የቀረውን ለማሽኑ ልታጎርሰው ያዘዘችውን
ፋይል በጉጉት እየተመለከተ
“ምንድነው የያዝሽው?” አላት፡፡

“ምንም አይደለም። ፅዳት እያካሄድኩኝ ነው::” አለችው እና ወረቀቱን ወደ ማሽኑ አፍ ከተተችው:: ማሽኑም ወረቀቱን እየሸረካከተ በዚያኛው ጎን
በኩል ሲተፋው ኒኪ “አታስብ ጠቃሚ የሆኑ የታካሚዎቼ ፋይሎች አይደሉም። ባልደረባህ መጥቶ ይህንን ሲያይ ይበልጥ የማያምንበት ነገር እንዳገኘ እንዳያስብ እና ይበልጥ እንደ ወንጀለኛ
ሌላ እኔን እንዳይመለከተኝ ደግሞ”

“እውነቱን ስለነገርሺኝ አመሰግናለሁ::” ብሎ ፈገግ አለ። ደግሞስ እንዲ
ዶክተር ኒኪ ያሉ ቆንጆ ሴቶች ፊት ሥርዓት ያለው ፖሊስ ሆኖ መተወን እንዴት ያቅተዋል?

“እና ቅዳሜ ምሽት እዚህ ምን እግር ጣለህ መርማሪ ፖሊስ ጉድማን?”
ብላ ማሽኑን እያጠፈች ጠየቀችው።

“ጠዋት ላይ ስለተፈጠረው ነገር ይቅርታ ልጠይቅሽ ነው የመጣሁት” አላት እና ውሸቱን በመቀጠልም መርማሪ
ፖሊስ ጆንሰን አንቺን እንደዚያ መናገር
አልነበረበትም።” አላት።

“መልካም” አለች እና ኒኪ በመቀጠልም “ግን እኮ ለጥፋቱ ይቅርታ መጠየቅ ያለበት እሱ እንጂ አንተ መሆን አልነበረብህም። አይመስልህም?”

ጉድማንም ትከሻውን ሰብቆ “እኔ እና እሱ ባልደረቦች አይደለንም። በዚያ
ላይ ደግሞ ለጥፋቱ ይቅርታ መጠየቅ አንደኛው የእሱ ችግር ነው እና እኔ
ልጠይቅለት ብዬ ነው” አላት።
ኒኪም ሳቀች እና “አሁን ገባኝ” አለችው። መርማሪ ፖሊስ ጉድማን ለማውራት ቀለል የሚል ሰው ስለሆነ ደስ ብሏታል “መቼስ እየዋሸሁ እንዳልሆነ ይገባሃል ብዬ አስባለሁ።” ብላ በማስከተልም “ባለፈው ምሽት እኔ የምኖርበትን ቦታ የሚያውቅ ሰው መኖርያ ሰፈሬ ድረስ መጥቶ በመኪና ገጭቶ ሊገድለኝ ነበር” አለችው፡፡

አምንሻለሁ” አላት እና ጉድማን በማስከተልም “ጆንሰንም ቢሆን
ያምንሻል። ምክንያቱም የምርመራ ቴክኒሽያኖችን ብዙ ብዙ ማስረጃዎችን
ከአካባቢው ላይ ሰብስበዋል”

“እውነትህን ነው?” ብላ ኒኪ የመገረም ፊት እያሳየች “ታዲያ ለምንድን ነው እኔን የቀን ቅዠተኛ እያለ የሚወነጅለኝ? እኔ ምን አድርጌ ነው?”

“እሱን እንኳን አላውቅም” ብሎ ለሰኮንዶች ያክል ዝም ብሎ ቆየ፡፡
ከዚያም “ምናልባት እኔ እና አንቺ ሆነን እሱ አንቺን ለምን እንደዚህ
እንደሚመለከትሽ ኋላ ላይ እንደርስበታለን፡፡ መጠጥ ልጋብዝሽ ዶ/ር
ሮበርትስ?”

ሎስ አንጀለስ ውስጥ ብዙ ሰው ወደማይበዛበት ጎዳና ታናስ ወደ ተባለ
ባር ይዟት ሄደ:: ኒኪ ጃክ ዳንኤልን አዘዘች እና ሲቀዳላት ብርጭቆውን
( ጉድማን አስተናጋጁ ሙሉውን ጠርሙስ ጠረጴዛው ላይ ትቶት እንዲሄድ
ሙሉውን መጠጥ በአንድ ትንፋሽ ጨለጠችው። በዚህም የተበረታታው
በምልክት ነገረው እና ትቶላቸው ሄደ፡፡

“ባለፈው ምሽት ላይ እኔን መኪና ገጭቶ ሊገድለኝ የነበረው ሰው ሊዛን እና ትሬይን የገደለው ሰው ነው ብለህ ታስባለህ?” ብላ በቀጥታ ጠየቀችው።

“ምናልባት እራሱ ወይንም እነርሱን ከገደለው ሰው ጋር ግንኙነት ያለው ሰው ነው ብዬ አስባለሁ ብሎ ጉድማን
መጠጡን ተጎንጭቶ ከመጀመሪያው ጊዜ ጀምሮ ገዳዩ አላማ ያደረገው አንቺን ነው ብዬ ነው የማምነው።” አላት፡፡

ኒኪ ለሊዛ ፍላንገን ባዋሰቻት የዝናብ ኮቷ የተነሳ ኒኪን መስላቸው በስህተት እንደገደሏት ጭምር ግምቱን ነገራት፡፡ በዚያ ላይ ባለፈው ማክሰኞ የተሞከረባት ግድያ የሚያመለክተው ኒኪ ከሊዛ እና ከትሬይ ጋር ባላት ግንኙነት ምክንያት ግድያዎቹ እንደተከወኑ ጭምር አስረዳት፡፡

“ልክ ነህ እንበል እሺ” ብላ ኒኪ በእርጋታ መለሰችለት እና “እሺ እነዚህ ሰዎች እኔን ለመግደል እየተከታተሉኝ ነው ልበል። ግን እነዚህ ሰዎች እኔን ለመግደል ለምንድነው የሚፈልጉት? ምንድነው ምክንያታቸው?”
“አሁን ላይ አንቺን ለመግደል ምክንያታቸው ምን እንደሆነ አላውቅም”
ብሎ ጉድማን በመቀጠልም “ግን ሊዛን እና ትሬይን የገደሉት ሰዎች ሁለቱንም ሰዎች አሰቃይተዋቸው ነው። ሰዎቹ ደግሞ ሰዎችን የሚያሰቃዩት
የሆነ መረጃን እንዲሰጧቸው ስለሚፈልጉ ነው። አይመስልሽም?” ብሎ
ጠየቃት፡፡

ኒኪም ለአፍታ ያህል ስታስብ ቆይታ “እኔም እንደዚያ አስቤው ነበር።
ግን ደግሞ ገዳዮቹ በሰዎች ስቃይ የሚደሰቱ ሳዲስቶች ቢሆኑስ?” ብላ
ጠየቀችው፡፡

ጉድማንም መጠጡ ያለበት ብርጭቆ ላይ እንዳፈጠጠ ይህም ሊሆን
ይችላል ብሎ አሰበ፡፡

“የሞቱት ሰዎች ላይ የሌለ የሞተ ሰው ህዋስ ተገኝቷል የሚባለው ነገር
እውነት ነው?” ብላ ኒኪ ጠየቀችው፡፡

ጉድማንም በጥያቄዋ በጣም ደንግጦ “ይህንን ደግሞ ማነው የነገረሽ?”

“ከኢንተርኔት ላይ አንብቤው ነው” ብላ ኒኪ በመቀጠልም “የዞምቢ ገዳይ በሚል ርዕስ ዙሪያ በኢንተርኔት ላይ ሰዎች ዜናውን እየተቀባበሉት ነው” አለችው፡፡
ጉድማንም በሰማው ነገር በጣም በሸቀ። ይህን የመሰለ መረቅ መረጃቸው ከእነርሱ አፈትልኮ ከወጣ በኋላ ደግሞ ነገሩ እየሰፋ ይሄድ እና የአሽሙር ጋዜጣ ገፆች ላይ ይወጣል ብሎ አሰበ፡፡

“እውነት ነው ነገሩ” ብላ ኒኪ ተጭና ጠየቀችው፡፡
👍1
“የሊዛ እና የትሬይ ገዳይ ዞምቢ ነው ተብሎ የሚወራው ነገር ውሸት ነው።” ብሎ ጉድማን ነገሩን ሊዘጋባት ሞከረ፡፡

“እና የሞተ ሰው ህዋስ በሟቾቹ ላይ አልተገኘም?”

“ስለ ምርመራው ዝርዝር ልነግርሽ አልችልም። ግን ይሄ ስለ ዞምቢ
የሚወራው ነገር የማይረባ ነው፡፡ ይልቅ እኔን ለምን መግደል ይፈልጋሉ?
የሚለው ጥያቄሽ ጥሩ ነው፡፡ ስለ ሳዲስትነት የተናገርሽው ነገር እንዳለ ሆኖ
እኔ ግን የማምነው ከግድያዎቹ ጀርባ የሚገኝ አንድ ሰው አንቺ የሆነ ነገር
እንደምታውቂ ያውቃል ብዬ እገምታለሁ። ይሄን ነገር ደግሞ ምናልባትም ትሬይ እና ሊዛ ያውቁታል ብለው ገዳዮቹ ያስባሉ። ይሄ ነገር ምን እንደሆነ አሁን ላይ እኔ ለማወቅ አልችልም። ምናልባት ስለታካሚዎችሽ ሊሆን ይችላል? የሆነ ሰው ተደብቆ እና ሚስጥር ሆኖ እንዲቆይለት የፈለገው ሚስጥር ሊሆን ይችላል? ወይንም ደግሞ ሟቹ ባለቤትሽ ያከመው እና ያዳነው ሰው ሚስጥር ሊሆን ይችላል... ግን ግምቴ” ብሎ ጉድማን ከመጠጡ በድጋሚ ተጎነጨ እና “ይህንን ገዳዮቹ እንዳይወጣባቸው የፈለጉትን ሚስጥር አንቺ እንደምታውቂ ነው::”

ኒኪም ግራ በተጋባ ፊት ጉድማንን እየተመለከተችው “ተሳስተሃል!
በእውነት ስለ እዚህ ስለምታወራው ነገር እኔ ምንም አላውቅም። ነገሩን ባውቅ እና ብረዳ ኖሮ ለእናንተ አልነግራችሁም ነበር እንዴ? እኔ እኮ ስለ ትሬይ በተለየ መንገድ ቢሆንም ስለ ሊዛ ደንታ አለኝ”

“ደንታ አለሽ?” ብሎ ቅንድቡን ቋጥሮ ጉድማን ጠየቃት፡፡

“አዎን ደንታ አለኝ።” ብላ ኒኪ በማስከተልም “ሙያዬ ለእሷ ደንታ
እንዲኖረኝ ያስገድደኛል፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ስለ እራሴም ቢሆን ደንታ
አለኝ፡፡ እኔ መገደል የምፈልግ ይመስልሃል? ቤቴ ደጃፍ ላይስ በመኪና
ተደፍጥጬ መሞት የምፈልግ ይመስልሃል? እመነኝ ይህ ነፍሰ ገዳይ
ቢያዝንልኝ ከማንም በላይ ልቤ ያርፋል፡፡ ገባህ መርማሪ ፖሊስ ጉድማን”

“ሎው ብለሽ ጥሪኝ” ብሎ ጉድማን ለሁለቱም መጠጥ ቀዳና “እንዴ አንቺ
በገዳዮቹ ለመጎዳት ፈልገሽ እንዳልሆነ እኮ ይገባኛል፡፡ ይሄ ሊያስገድልሽ
የሚያስችለውን ነገርንም በግልፅ ታውቂያለሽ ማለቴ አይደለም፡፡ ግን በድብቁ የአዕምሮ ክፍልሽ ውስጥ ይሄ ነገር ተደብቆ ተቀምጧል። የዚህን እንቆቅልሽ መፍቺያ ቁልፍ ከአንቺ ጋር ይገኛል እና ቁልፉን ስታገኚው ነገሩ ሙሉ
በሙሉ ይፈታል ማለት ነው።” አላት፡፡

ብርጭቆውን አንስቶ መጠጡን ሲጎነጭ ኒኪም ብርጭቆዋን አንስታ መጠጧን ተጎነጨች። የሆነ የሞቅታ ስሜት እየተሰማት ነው። የተነጋገሩት
ነገር ሞቅታን ይልቀቅባት ወይንም ደግሞ መጠጡ እርግጠኛ አይደለችም::በዚያ ላይ ደግሞ እሱ ይሁን ወይንም እሷ ከሁለት አንዳቸው እጁን ቀድሞ
ሰድዶ ጣቶቻቸው ተቆላለፉ። ጣቶቻቸው ሲቆላለፉ ወደ ብልቷ አካባቢ ሞቅ
አላት። በተለይ ደግሞ ቀና ብላ ስታየው ከንፈሩን ምጥጥ አድርገሽ ሳሚው
ሳሚው የሚል ስሜት መጣባት። ይሄው ከብዙ ወራት በኋላ የወሲብ ስሜቷ
በጤነኛ መልኩ ስለተቀሰቀሰባት ደስ ብሏታል። ምክንያቱም ለአኔ ቤታማን
የሚሰማት ስሜት ሁሌም ግራ ይገባት ነበር።

እሱም ቢሆን ለእሷ የሆነ ነገር እንደተሰማው አይኑ ውስጥ
ያስታውቅበታል። ድምፁም ቢሆን ይሄንን ጥያቄ ሲጠይቃት ትንሽ ሻከር
ብሎበት ነበር።

“ለምንድንነው ሳይኮሎጂስት ለመሆን የፈልግሽው?” ብሎ ጠየቃት።
ይህንን ጥያቄ ከእሱ የምትጠብቀው ጥያቄ ስለነበርም ፈገግ አለች እና
“ምናልባት ተመሳሳይ እና አሰልቺ ሥራን የሚሠራ ባለሙያን መሆን ስላልፈለኩኝ ይሆናል፤ አለ አይደል የህግ ባለሙያ ወይንም አካውንታንት ከመሆን ይሄንን መረጥኩኝ። የመድህኒት ነገሮች ደስ አይሉኝም። ደም ማየት በጣም ስለምፈራ ደግሞ የቀዶ ጥገና ሀኪም መሆን አልችልም”

“እንደዚህ ድንጉጥ ነገር ነሽ እንዴ?” ብሎ እያሾፈ ጠየቃት፡፡

“እንደዚያ ነገር” አለች እና ትንሽ አፍራ “አንተ ለምን ፖሊስነትን መረጥክ?”

“ኸ” አላት እና ጉድማን ወንበሩን ደገፍ አለ እና ስሜቱ እና ፊቱ ላይ የሚታየው ነገር ትንሽ ከተለወጠ በኋላ “መልካም እንግዲህ... ይመስለኛል ወንጀለኛ እና መጥፎ ሰዎችን ከድርጊታቸው ለማስቆም በማሰብ መሰለኝ ፖሊስ የሆንኩት፡፡ የሆነ የደነዘ መልስ መለስኩልሽ መሰለኝ?”

ኧረ መልስህ በፍፁም የደነዝ መልስ አይደለም” አለችው።

“ህፃን እያለሁ የሆኑ ሰዎች አባቴን አታለውት ሀብቱን እንዲያጣ
አደረጉት” አላት እና ጉድማን ቀጥሎም “የሆነ የማይሆን የውሸት ድርድር
ውስጥ እንዲገባ ካደረጉት በኋላ ሁሉንም ነገሮቹን እንዲያጣ አደረጉት።
መኖሪያ ቤታችን እና ትዳሩንም እንዲያጣ አደረጉት፡፡ እነዚህን ሰዎች
እጠላቸዋለሁ።”

“ይገባኛል የምትለው” ብላ ኒኪ ራሷን በአዎንታ ከፍ ዝቅ ካደረገች በኋላም ወደ እሱ ዘንበል አለች። መጠጡ ምላሱን ትንሽ ያዝ ቢያደርገውም እየተናገረ ያለው በስካር መንፈስ እንዳልሆነ፣ ትክክለኛውን የሚሰማውን ስሜቱን መሆኑን ለማየት ችላለች “እሺ አባትህ በድጋሚ አግብቶ ኑሮውን መኖር ጀመረ?” ብላ ጠየቀችው::
ጉድማንም በጥያቄዋ የምሬት ሳቁን ሳቀ እና “የአሥር ዓመቴን ባከበርኩኝ በሳምንቱ ጋራዦችን ውስጥ በጋዝ አፍኖ ራሱን አጠፋ።በሚቀጥለው ቀንም ቤታችን እና መኪናችን ለጨረታ ቀረበ።” አላት፡፡

ኒኪም በሰማችው ነገር ልቧ ተነክቶ “በጣም ይቅርታ ሉው።በእግዚአብሔር ሥም ወደ ኋላ መልሼ አሳዘንኩህ።” አለችው፡፡

ፊቱንም በእፍረት በእጁ ሸፍኖ ከዚህ ጨዋታ ለመውጣት በሚያሳብቅ
ስሜት ውስጥ ሆኖ “ችግር የለውም አትጨነቂ፡፡ ነገሩ በእርግጥ በጣም
አሳዛኝ ነገር ቢሆንም ፖሊስ ለመሆን ያነሳሳኝን ገጠመኝ ሰጥቶኛል። ፖሊስ
መሆን ብቻ ሳይሆን ገጠመኙ ያስተማረኝ ገንዘብ ምን ያህል አስፈላጊ ነገር
እንደሆነም ጭምር ነው። ማንም ሰው እኔን እንዲቆጣጠር እንዳልፈቅድም
አድርጎኛል። የእኔ ህይወት አለቃ እኔ ነኝ አይደል?”

ምንም እንኳን መጨረሻ የተናገረው ነገር እውነት እንደሆነ እርግጠኛ ባትሆንም ኒኪ ራሷን በማስማማት ነቀነቀችለት፡፡

“ሊዛ ከመሞቷ ከወራቶች በፊት የገጠሙሽ የተለዩ እንግዳ የሆኑ ነገሮች
እንዳሉ ማስታወስ ትችያለሽ?” ብሎ ጠየቃት ጉድማን ወሬያቸውን ወደ እሱ
ጉዳይ ለመመለስ በማሰብ፡፡

ኒኪም አይኗን ጨፍና እጁንም ጨመቀች፡፡ ወደ እሱ በጣም ያቀረባትም
መሰላት፡፡ ምክንያቱም የልጅነት ሚስጥሩን ሳይደብቅ አምኖ ነግሮኛል ብላ ታምናለች።

“ሊዛ ላይ ወይንስ እኔ ላይ?” ብላ ጠየቀችው፡፡

"ሁለታችሁም ላይ''

መልካም” ብላ ኒኪ ምራቋን ዋጠች እና “ሊዛ ለዊሊ ባደን ግንኙነታቸው
ማብቃት እንዳለበት ነግራው ነበር። ይሄ ያልተለመደ ነገር ነው?”

ጉድማንም “እሺ የአንቺን ንገሪኝ?” አላት፡፡

ኒኪም አይኗን ገለጠች እና አይኑን ትክ ብላ እያየችው
“እኔን ከገጠሙኝ በጣም አስገራሚ ነገሮች ውስጥ አንዱ ደግሞ ባለቤቴን
በሞት ማጣቴ ነው” አለችው፡፡

ጉድማንም ጣቶቿን ወደ ከንፈሩ ወስዶ ሳማቸው፡፡

ከባሩ ኋላ ተቀምጦ ኒኪ እና
ጉድማን እጅ ለእጅ ተያይዘው
የሚያደርጉትን ነገር የሚከታተል አንድ ሰው አለ።

ይህቺ ሴት ይህንን ሰው በምትፈልገው መልኩ እየቃኘችው ነው ብሎ ጉድማን የኒኪን ፀጉር እየዳበሰ እና አፉ ለመሳም ሲከፈት የተመለከተው ሰውዬ በውስጡ አሰበ፡፡ በመቀጠልም ምንም አይነት አሳዛኝ ታሪክ ነግራው ቢሆንም ያሰበችው ተሳክቶላታል አለ ሰውዬው አሁንም በሃሳቡ፡፡ ሁለቱንም እየተመለከተ፡፡ በእውነቱ ይህቺ ሴት ይህንን ሰው በጣም እያሞኘችው ነው ጉድማን ለመጠጡ ሲከፍል የተመለከተው ሰውዬም ቢራውን ጨለጠ፡፡

ዶ/ር ሮበርትስ እና ጉድማንም ልክ እንደ አፍላ ወጣቶች እጅ ለእጅ ተያይዘው በሳንታ ሞኒካ ጎዳና ላይ ሲራመዱ ተመለከተ።
👍1🔥1
ተመልካች ብቻ ሆኖ መቅረት እና ምንም ነገር ማድረግ አለመቻሉ ጭንቀትን ፈጠረበት።

ሰውዬው ራሱን የድርጊት ሰው አድርጎ ነው የሚያስበው። ግን ያለፉት ጥቂት ሳምንታት ነገሮችን በትዕግስት ተሞልቶ መከወን ጥሩ ነገር እንደሆነ ትምህርት ወስዷል። ደግሞስ ከዚህ በኋላ ለነገሮች ሁሉ ዘገምተኛ ሆኖ መቆየት እንደማይችል ስለሚያውቅ ትንሽ ተፅናና።

ከዚህ በኋላ መመልከት ብቻ ሳይሆን ማድረግም ይችላል፡፡ ለዚያውም
በጣም በቅርቡ...

ይቀጥላል
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ


....የክፍሉ ፀጥታ ክመቃብር ከበደ፡፡

“በዛን ወቅት መንገዱን አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ
በዳ የሚጮህ ሰው ድምፅ ነበር፡፡” ሰውየው ቀጠሉ… “የከማሪካው ልጅ!
የጋናው ነብይ ንክሩማ 'ዋ! ነበር ያለው ዋ! ከፊታችን የተጋረጠውን የአፍሪካ ችግር ተባብረን በአንድነት ከመጋፈጥ ወደኋላ ብንልና ተበታትነን ብንቆም በድጋሚ በሌላ የቅኝ ግዛት ስር ወድቀን ለከፋ ምሬትና ሰቆቃ መከተል መሣሪያ እስክንሆን ድረስ እርስ ሰርሳችን ስንጎነታተልና
ስንቦጫጨቅ እንቆያለን፡፡ ነበር ያለው፡፡”

“ተሳስቶ ኖራል ያ ሰው? ተሳስቶ ኖራል ያ ነብይ? ”

ሽማግሌው መልስ ይፈልጉ ይመስል በክፍሏ ውስጥ የተሰበሰቡትን
ሁሉ በተራ ተመለከቷቸው፡፡ ተጠባበቁ፡፡ መልስ አላገኙም፡፡

“ዛሬ ምን እያደረግን ይሆን?!ያ ሰው እንዳለው እርስ በርሳችን እየተጎናታልን አይደለም? ዛሬ ምን እያደረግን ይሆን? . እርስ በርሳችን እየተቦጫጨቅን አይደለም? ያኔ ክዋሜ ንክሩማን ተቃውመው የቆሙ የሪጅናል ውሀደት አቀንቃኞች የጥንቃቄና የእርጋታ መነኮሳት የት ገቡ? ዛሬ ምን ይላሉ? ምነው ድምፃቸው ጠፋ? በከፋ የቅኝ ግዛት ስር! በረሃብና በድንቁርና ስር በእንብርክክ የሚድኸው የዛሬው የአፍሪካ ህዝብ ተጠየቁ ቢላቸው ያ ሰው ተሳስቶ ነበርን? ቢላቸው ምን ይሆን መልሳቸው?”

አዛውንቱ ለአፍታ አቀርቅረው ቆዩ፡፡ መልሰው ቀና ሲሉ ፊታቸው
እልህና ቁጭት ለብሶ ነበር፡፡

“ለወቀሳ ጊዜ የለንም፤ለቁጭት ጊዜ የለንም ለምሬት ጊዜ የለንም ፤ሰላሳ ዓመት አምጠናል፡፡ እንወልዳለን ቆንጆ ቆንጆ ልጆች፡፡ ዛሬ እዚህ የተሰበሰባችሁ ሁሉ እዋላጆች ናችሁ፡፡ አዲስ የመጣችሁትን እንኳን ጨለማው ተገፈፈላችሁ እላለሁ፡፡ በተረፈ ከፊት የምንጋፈጠውን ሁሉ በሙሉ ልብ ልትቋቋሙት ቃል ትገባላችሁ፡፡”

ርብቃ የገባችው ቃል ምን ያህል አስፈሪና ጥልቅ እንደሆነ እየሰረፀባት የመጣው ጊዜ ከሄደ በኋላ ነበር፡፡

“ብዙ አወራሁ” አሉ ሽማግሌው : ዝግጅቱ አልቆ ሊሄዱ ሲነሱ
“ስለአፍሪካችን ሲነሳ ብዙ ዝም ማለት ይቀናኛል፡፡ እኔ ብቻ ሳልሆን እኩዮቼ
ሁሉ በዕድሜያችን ያየነው ልሳን የሚያደርቅ ነው፡፡ ዛሬ ግን ሃላፊነቴን
መወጣት ነበረብኝ፡፡ ብዙ አወራሁ:: ይበቃል፡፡”

ተነሱ፡፡

በክፍሉ ውስጥ የነበሩት ሁሉ ተነስተው ቆሙ:: ሰውየው በክፍሉ ውስጥ ያሉትን ወጣቶች በተራ ጨብጠው ሲያበቁ አብረዋቸው ከመጡት በዕድሜ ከሚቀርቧቸው ሰዎች ጋር ተከታትለው ወደ በሩ አመሩ፡፡ ከክፍሉ ከመውጣታቸው በፊት ቆም አሉና በክፍሉ ውስጥ ሰብሰብ ብለው በአክብሮት የሚመለከቷቸው ወጣቶች ላይ አተኮሩ…

“ተጠንቀቁ!” አሉ አዛውንቱ ፈገግ ብለው፡፡ “እዚህ ያወራነውን ጮክ ብላችሁ አታውሩ። አፍሪካችን ተኝታለች። እንዳትባንን፡፡”

ርብቃ ወዲያው የተሰጣት ትዕዛዝ ወይም ኃላፊነት አልነበረም፡፡
“ጊዜው ሲደርስ ስትፈለጊ ትጠሪያለሽ፡” ተብላ ቆየች፡፡ ቢሆንም በወር አንዴ እሷ የምትገኝበት ህቡዕ ህዋስ በሚያደርገው ስብሰባ ላይ እየተገኘች ስለአፍሪካ ሁለገብ ችግር የሚደረጉትን ውይይቶች ስትካፈል ቆየች፡፡

ከሁለት ወር በኋላ ነበር የመጀመሪያው ትዕዛዝ በምሥጢር የተላሰፈላት፡፡ በሬድዮ “የአፍሪካ ምጣኔ ሃብት” በሚል ርዕስ ሣምንታዊ ኘሮግራም እንድታዘጋጅ ተነገራት፡፡ በመጀመሪያ ሃሳዑን ለአለቃዋ እንዴት እንደምታቀርብ ቸግሯት ነበር፡፡ ነገር ግን በማግስቱ አለቃዋ እራሳቸው
እቢሮኣቸው ድረስ አስጠርተዋት ማክሰኞ ማታ የሚቀርበው የሙዚቃ ክፍለ
ጊዜ ስለሚቋረጥ በምትኩ ሊቀርቡ የሚችሉ ፕሮግራሞች ሰብስሲና
እንነጋገርባቸዋለን፡፡” አሏት፡፡

ደነገጠች፡፡ ነገሩ ገባት፡፡ አባል የሆነችበት ህቡዕ ድርጅት ምን ያህል ውስጥ ለውስጥ ስር የሰደደ እንደሆነ ተገነዘበች፡፡

“እ...የአፍሪካ ምጣኔ ሃብት
ላይ… ” አለች ሳታውቀው፡፡

“ግሩም” አሉ አለቃዋ ፈገግ ብለው ከመቀመጫው እየተነሱ እየጨበጧት፡፡ “በርቺ፡፡ ማንኛውም ችግር ሲገጥምሽ ቀጥታ እኔጋ ነይ፡፡ አይዞሽ፡፡”

ከአለቃዋ ቢሮ ስትወጣ ጉልበቶቿ እየተብረከረኩ ነበር፡፡ ሃላፊነቱ
ከወፍጮ ከብዶ ታያት፡፡

ሁለተኛው ትዕዛዝ ከሁለት ወራት በኋላ ተከተለ፡፡
“እና ምንድነው ማለት ነው የማደርገው?”

ባጭሩ በፈለግሽው መንገድ በእህትነትም ፡ ሆነ በሌላ ታጠምጅዋለሽ እንዳልኩሽ በውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በአፍሪካ ጉዳይ ቢሮ ውስጥ ሁለተኛውን ወንበር የያዘ ሰው ነው::እያንዳንዱን ነገር ለማግኘት እንፈልጋለን፡፡በተቻለሽ እለቢው... እ..ቤቱ ይዟቸው የሚመጡ ወረቀቶችን አጥኚ፡፡ ያገኘሽውን ሁሉ፡፡ ከዚህ በተረፈ…በየጊዜው ተጨማሪ መመሪያ ይተላለፍንልሻል።” የህቡዕ ህዋሷ መሪ ነበር ማርቆስ፡፡

“እንዴት ነው ሰውየውን የማገኘው? ማለቴ

የሚቀጥለው ቅዳሜ ሶስና የልደት በዓሌ ነው ብላ ትጠራሻለች ግብዣው ላይ ትገኛለሽ አብረው ስለሚሰሩ እሱንም ትጠራዋለች፡፡ ታስተዋወቅሻለች። ከዚያ በኋላ እኔና አንቺ እየተረዳዳን እንቀጥላለን፡፡” ትከሻዋን ቸብ አድርጎ ተነሳ “በነገራችን ላይ የሰውዬሽ የምሥጢር ስም "ዱርዬወ" ነው:: ገባሽ? '
ዱርዬው ” አለ ማርቆስ በጠባሳ የተገመሰ ፊቱን በቀኙ ፈተግ አድርጎ “ተግባባን?”
“ገባኝ፡፡”

እንደተባለችው ሶስና በልደት በአሏ ላይ አስተዋወቀቻቸው፡፡ ናትናኤልን “ዱርየው”ን የህዋሷ መሪ ማርቆስ እንዳላት መረቧን ዘርግታ ፍቅረኛዋ አደረገችው፡፡ ሰርስራ ሕይወቱ ውስጥ ገባች፡፡ ምስጢሯን ነግራው
ምረሥጠርህን አለችው:: ያገኘችውን ሁሉ አሳልፋ ሰጠች፡፡ ጊዜ ሲሄድ እሷው ያዘጋችው መረብ እሷኑ ተቀተባት፧ አደናቀፋት፤ ወደደችው፡፡ሆኖም ሳታቋርጥ ቡድኑ መረጃዎችን ስታቀብል ቆየች፡፡ ይህ ብዙም አላሳሰባትም:: ምክንያቱም ናትናኤል ለአፍሪካ የነበረው ግለት ከማናቸውም የደበዘዘ አልነበረም፡፡ ለዚህም ነበር ላህዋሷ መሪ በሳምንት አንዴ በምታቀርበው ዘገባ ላይ ዱርዬው' በህቡዕ ድርጅቱ ውስጥ ቢመለመል ጉዳት እንደማያስከትል ደጋግማ ያመለከተችው፡፡ ለምን እንደፈሩት ባይገባትም ምክሯን ሊጠቀሙበት አልወደዱም፡፡ ቢሆንም እንደዚህ ዓይነት ነገር ውስጥ ይገባል ብላ ጠርጥራም አታውቅ፡፡ ናትናኤልን እንደ ወንጀለኛ ማሳደድ! መጀመሪያ ነገር ነፍስ ማጥፋትንስ ምን አመጣው? ጓደኝየውንስ ለምን ገደሉት? ፈጣሪዬ የት ገብቶ ይሆን የተሰወረው? እውነት ቢያገኙት አይጎዱትም ይሆን? እንዴት ልታምናቸው ትችላለች? ቢገድሉትስ? ቢቀር
ይሻላል፡፡ እንዲይዙት ብትረዳቸውና አይኖቿ ስር አንድ ነገር ቢያደርጉትስ?
ገብሬልዬ፤ ግን ደግሞ ራሳቸው ፈልገው ቢያገኙትስ? ዘገነናት፡፡ ዘገነናት
ያለፈው ትዝታ ሁሉ መጣባት::እና ቀና ብላ ተመለከተችው በሩ አጠገብ ካለ ወንበር ላይ ተቀምጦ እያከታተለ በላይ በላዩ ሲጋራ የሚያጨሰውን ሰው፡፡ በትዝብት መልሶ ተመለከታት:: ባንዳ!' ያላት መሰላት ድጋሚ።

“ማርቆስ” አለችው አይኖቿ ላይ እንባዋ አቆርዝዞ፤ “ማርቆስ ግን ምን አደረጋችሁ? ናትናኤል'ኮ ምንም አያውቅም፡፡ ማርቆስ እውነቴን ነው፣ ምንም አያውቅም:: እመነኝ አብረን ብዙ ሰርተናል፡፡ አውቅሃለሁ ታውቀኛለህ:: አልዋሽህም:: ምንም አያውቅም ናትናኤል፡፡”

“ነገርኩሽኮ:: ምንም እንደማያውቅ እኛም ደርሰንበታል፡፡ ግን ሊደርስበት ወደማይገባ ቁልፍ እያነፈነፈ እየተጠጋ ነው።ሊያገኘው ይችላል። ሰውዬሽ ቀላል ሰው አይደለም፡፡ ምሥጢሩን ካገኘ ደግሞ ዕቅዱ ሁሉ እጁ ገባ ማለት ነው፡፡ያ ደግሞ ለእኔና ለአንቺ ብቻ ሳይሆን ለሁላችንም
ለአፍሪካ…ውድቀት ነው ብጥብጥ ነው…ሁከት ነው፡፡ማንም ይቅርታ አያደርግልንም፡፡አንድ በአንድ በየአገሩ እየታደንን በየአገሩ
👍3
እየተመነጠርን እንንጠለጠላለን ሲጋራውን ምጥጥ አድርጎ ከተቀመጠበት ተነሳና መተርኮሻው ላይዐደፈጠጠው፡፡ “ያ ከመሆኑ በፊት እጃችን መግባት አለበት፡፡ አፍሪካ በደም ከመዘፈቋ በፊት፧ በሺህ የሚቆጠሩ ንፁህ ልጆቿ ከመታረዳቸው በፊት ናትናኤል መያዝ አለበት፡፡”
“ይመልመል ስላችሁ ቢመለመል ይህ ሁሉ አይመጣም ነበር።
ናትናኤል የአፍሪካን ችግር ከማንኛችንም እኩል የተረዳ ሰው ነው በራሳችሁ ጥፋት…በገዛ ራሳችሁ ዳተኝነት ዛሬ በማያውቀው ምሥጢር ታሳድዱታላችሁ፡፡ ያኔ ቢመለመል ኖሮ እንዳልኳችሁ ቢመለመል ኖሮ…”

“ርብቃ ንገረኝ ካልሽ እነግርሻለ ናትናኤል ያልተመለመለበት ምክንያት አለው ወኔ ቢስ ነው፡፡ፈሪ ነው ማለቴ አይደለም፡፡ ያንን አላውቅም።ግን ስልብ ነው!ለስልሷል ቦቅቡቋል፤ በነጮች ቅራቅንቦ ላሽቋል፡፡ርብቃ እመኝኝ በርካታ የናትናኤል ብጤ የትማሩ አፍሪካውያን የአፍሪካን
ችግር ሳይረዱት ስለቀሩ አይምሰልሽ ዋጋ ቢስ የሚሆኑት፡፡ የራሳቸው ሚዛን
ስለሌላቸው በነጮች መስሪያ በነጮች ሚዛን ስለታወሩ ነው...

“ጆሞ ኬንያታ እንዳለው ከዘመናት በፊት ነጮች ክርስትናን እየሰበኩና ስለሰማያዊው መንግሥት እያወሱ የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያሉ በግራ ወንጌል እንግበው በቀኝ ጠመንጃ ጨብጠው ገቡ የምድሩን ተውት'አሉ፡፡ ዋናው የሰማዩ ነው አሉ፡፡ ቀኙኝ ሲያጉኗችሁ ግራውን ስጡ አሉ፡፡ አመንናቸው፤ተንበርክከን ጭንቅላታችንን
ደፋን፡፡ አልፍተውን አላሽቀውን ሲጨርሱ በተርታ ኣሰልፈው ለባርነት ሽጡን! ለዘመናት እንደ በግና ፍየል ጥጃና ግመል ወይፈንና ግመል ላትና ሻኛችንን ደንደስና ፍርምባችንን እያማረጠ ሽጡን ሽመቱን፡፡

“ዛሬ ደግሞ የተገላቢጦሽ ስለዲሞክራሲና ስሰሰው ልጅ መብት
ሊሰብኩልን ተነሱ፡፡ ያለፈው ሁሉ ተረሳና የዕሩን ሁሉ ተዘነጋና ስለበጎውና
ስለትክክለኛው መንገድ ሰባኪዎቹ ዛሬም እነሱው ሆነ፡፡ ቃል ኪዳናቸውን
ሰብረው ወንጌልን በሰበኩበት አፋቸው . ገበያ አውጥተው : : በዋጋ
እንዳልተከራከሩብን ዛሬ ድጋሚ ቅዱስ መስለው ረኲሳችሁ አሉን፤ የሰው
መብት አፍሪካ ውስጥ ተረገጡ አሉ፡፡ አፍሪካ ውስጥ ዲሞክራሲ
ድምጥማጠ ጠፋ አሉ፡፡ እነ አምኔስቲ ኢንተርናሽናል የዛሬዎቹ ሚሽነሪዎች
ሆኑ፡፡ በግራ ዲሞክራሲን በቀኝ ብድርና ዕርዳታ አንግበው ድጋሚ መጡ፤

የዲሞክራሲን መንገድ አዘጋጁ ፖለቲካውንም አቅኑ አሉ:: 'ኤኮኖሚውን
ተውት፤ ተደጋግፎና ተረዳድቶ ስለመስራቱ ስለማደጉና ስለመበልፀጉ
አትጨነቁ አሉ፤ ስለኋላቀርነታችሁ አትመራመሩ አሉ፤ መጀመሪያ
ዲሞክራሲ አሉ መጀመሪያ የሰው ልጅ መብት፤ መጀመሪያ የራስን ዕድል
በራስ መወሰን አሉ...

“የሚያሳዝነው ግን የእኛ ድጋሚ መታለል ነው?” ድጋሚዐእየተንበረከክን ድጋሚ ጭንቅላታችንን እየደፋን መሆናችን ነው::

“ቴዎድሮስ ከአንድ ምዕተ ዓመት በፊት ያለውን ታስታውሻለሽ በመጀመሪያ የሃይማኖት ሰባኪዎችን ትልክላችሁ፡፡ ቀጥሎ እነሱን የሚጠብቅ ቆንሲል፡፡ ቆንሲሉን ለመጠበቅ ደግሞ ወታደሮቻችሁን፡፡ በመጨረሻ አገራችንን ትወስዳላችሁ ነበር ያለው፡፡ ርብቃ የዛሬም ስልታቸው የተለየ አይምሰልሽ፡፡ ዲሞክራሲን ይሰብኩናል፡፡ ቀጥሎ እሱኑ ማጠናከሪያ ብድርና ዕርዳታ ያጎርፋልናል፡፡ ብድርና እርዳታውን ወጤታማ ለማድረግ ተብሎ ደግሞ በኤኮኖሚያችን ገብተው መሪ ቀያሽ፤ ደጋፊ ኣማካሪ፤ፈላጭ ቆራጭ
ይሆናሉ፡፡ በመጨረሻ አድቅቀውን እላቁጠውን ሲያበቁ ተረጅ ተደጋፊ ለማኝ
ተመዕዋች ያደርጉናል፡፡እምቢ ካልንና ተንኮል ሽራቸውን ቀድመን ካወቅንባቸዉ እርስ በርስ በዘርና በሃይማኖት እያጎናተሉና እያስታጠቁ እያራገቡ ያጨፋጭፉናል ! ሳንወድ በግድ ያንበረክኩናል፧ አንገታችንን ያስደፉናል፡፡ ሃቅና ሀስቱን አማተው አገለባብጠው: እኛነ፡ እራሳችንን ያስወቅሉናል፧
ሳናውቅ ሳንጠረጥር ነጭ አምላኪ ያደርጉናል፡፡ የነሱ ጨቋኝነት ወደ ጎን
ተብሎ እኛኑ ጨቋኝና ተጨቋኝ ብለው ያለያዩናል፡፡

“አፍሪካውያን ለሁለተኛ ጊዜ በነጮች ተበልጠናል፡፡ ለዘመኑ ሃይማኖት ለዲሞክራሲ ለዘመኑ ሚሽነሪዎች በነጭ ጋዜጠኞች ተበልጠናል፡፡ለዘመኑ የኤኮኖሚ ጦረኞች ለአይ.ኤም. ኤፍ.! ለዓለም ባንክና ለሌሎች ተንበርክከናል፤ አንገታችንን ደፍተናል፡፡ ዳግማዊ ሞት ሞተናል፧ ዳግማዊ ትንሳኤ ያሻናል፡፡

“ሬሳው የሚሸትና የሚከረፋው ሬሳው ያልተማረውና ያላወቀው ምስኪን አፍሪካዊ አይምሰልሽ፡፡ በተማርነውና አወቅን ሰለጠንን ባልነው ይብሳል ድሮም ጥቁር... ድሮም አፍሪካ.. ብሎ ነገር የሚጀምረው አወቅሁ ባይ ስልጣን አፍሪካዊ ይብሳል፡፡ ሳንጠረጥር ሳናውቅ ሳንሰማ ሰልበውናል፡፡”

“ለዚህ ነው ናትናኤል ሊመለመል አይችልም ያልኩሽ፡፡ ወኔ የለውም ስልብ ነው ያልኩሽ፡፡ አብሮን ሊሰለፍ የሚችል ለዘመኑ ሃይማኖት ያልተንበረከክ፣ አንገቱን ያልደፋ ኩሩ አፍሪካዊ ብቻ ነው መጀመሪያ አፍሪካ፤ መጀመሪያ የተባበረች አንድ አፍሪካ፤ መከፈል ያለበት ሁሉ ይከፈል ግን አንድ አፍሪካ የሚል መሆን አለበት፡፡ ተግባባን?” ማርቆስ በውስጡ
ያመቀውን ሁሉ የተነፈሰና የቀለለው ይመስል ተመቻችቶ ተቀምጦ ሲጋራ
ፍለጋ ኪሱ ገባ፡፡”

“አልገባኝም…” አለች ርብቃ አፍንጥጣ እየተመለከተችው “ምኑ ላይ ነው የናትናኤል ወኔ ቢስነት ታዲያ? ዲሞክራሲ ምኑ ላይ ነው ችግር የፈጠረው? ዲሞክራሲ በአፍሪካ መስፈኑ ምኑ ላይ ነው ጉዳት የሚሆነው፤ በዘመኑ ሃያማኖት እያልክ የምትኮንነው?”

“አየሽ አንቺም ሳታውቂው መተብተብሽን? ርብቃ ከዘመናት በፊት ነጮች ለአፍሪካውያን የሰበኩት ክርስትና አጥፊና ጎጅ ሆኖ ይመስልሻል የማታ ማታ ለባርነት የተዳረግን? አይደለም፡፡ ክርስትና ሃስትና ማወናበጃ፣ ክርስትና ማታለያ ሆኖ አልነበረም፡፡ እውነቱ ግን ነጮች ክርስትናን ወንጌልን መሣሪያ አድርገው፣ መሽፋፈኛ አድርጎ ሊያዘናጉን መቻላቸው
ነው፡፡ ወንጌልን እንስበክ ብለው ገብተው ውስጥ ገመናችንን ሊሰልሉ፣ሊያውቁ፣ ሊያጠኑንና ሊለያዩን በመቻላቸው ነው ፤ . ቀበሮ ሲሆኑ በግ መስለው በመምጣታቸው ነበር፡፡ ርብቃ ዛሬም ዲሞክራሲ ማታለያ አጥፊና
ጎጅ ሆኖ አይደለም:: ምሥጢሩ ግን በዲሞክራሲ ሰበብ እርስ በርሳችን
እየለያዩ እያቧጨቁ ማፋጀታቸው ነው፡፡ ለያይተው በታትነው አዳክመው
ድጋሚ ሌሽጡን ሊሸምቱን መነሳታቸው ነው፡፡ ከዘመናት በፊት ክርስትናን
እንደተጠቀሙበት ዛሬ ዲሞክራሲን ማንሳታቸው ነው፡፡”

“እና ምን ማድረግ አለብን?”

“መጀመሪያ አፍሪካ ማለት አለብን፡፡ መጀመሪያ አንድነታችን ማለት አለብን፡፡ ያ ብቻ ነው ጥንካሬያችን፡፡ ያ ብቻ ነው ብርታታችን፡፡ ያን ጊዜ አፍሪካ አንድ ስትሆን እንደዛሬው የሃምሳ አገሮች ሹክሹክታ ሳይሆን የአንድ አፍሪካ ድምፅ ያስገመግማል፡፡ ያን ጊዜ ዓለም ያዳምጠናል፡፡ ያን ጊዜ ብርታታችንን ይገነዘቡታል፡፡ አፍሪካችን ገና የምትለማ ነች ይህን አንሱ ያንን አፍርሱ ስላሉን ሳይሆን የሚበጀንን እንገነባለን የማይጠቅመንን እናፈርሳለን፤ አፍሪካችን ሰፊ ገበያ ነች ይህን በዚህ ሽጡ ስላሉን ሳይሆን በሚያዋጣን እንሸጣለን፤ ይህን በዚያ ግዜ ስላሉን ሳይሆን በሚስማማን
እንሸምታለን፡፡ አፍሪካ ድንግል ናት፤ ጥሬ ሃብት የእኛ ነው፤ከፋኝ ሲሉ እናበላልጣቸዋለን፧ አቃረን ቢሉ እናማርጣቸዋለን፡፡

“ያን ጊዜ ዛሬ የተላለቁብን ዛሬ የተዛባበቱብን የገላችንን ቀለም
አይተው አድፍ ፤ ኋላቀርነታችንን ገላምጠው ዝንጀሮ ያሉን ሁሉ
ወዳጅነታችንን ይመኙታል፤ ወንድማማችነቱን ያከብሩታል፡፡ አይ ቢሉ
አሻፈረን ቢሉ ሊገፉትና ሊገድቡት የማይደፍሩት ጎርፍ ሊዝቁት ሊጨርሱት የማይሞክሩት የባህር አሸዋ ጥቁር ሕዝብ ከፊታቸው እንደተጋረጠ ይገነዘባሉ ያኔ ነው ዲሞክራሲ ያኔ ነው የሰው ልጅ መብት ያኔ ነው የራስን
👍3
ዕድል መወሰን... ርብቃ ያ ጊዜ መጥቶ እልሄንና
ቁጭቴን እንደወጣ ነው ፈጣሪን የምለምነው ያ ነው ጸሎቴ ፡፡”....

💫ይቀጥላል💫
#የእናቴ_መዳፍ

እኔና እናቴ . . .
ከ'ለታት ባ'ንድ ቀን
ከትንሽ ቤታችን
ከትልቅ ልቧ ጋር ፤
ዐይን ዐይኔን እያየች
በሥሥት ፣ በፍቅር
ኾኜ ከእግሯቿ ሥር።

ትላንቷን ዐሰበች ፤ ትዝታ ትላንቷን
አምና ጨቅላነቴን ፣ አምና ጉብሊቷን።
ውብ ለጋ ነበረች ...!
ፍጹም ድንቅ ረቂቅ
የነፍሴ ሥንቅ ሐቅ
የቁንጅና ዕንቍ ፣ መግነጢሰ ውበት
የቀይ ዳማ ቅኔ ፣ የምናብ ሠገነት።

እምዬ ...

ትላንት . . .
ስንቱ ጎበዝ ፣ ደጅ ጠንቶ
ስጦታ ሸክፎ ፣ ዐሪቲውን ገዝቶ፣
ስንቱን ቆነጃጂት ፣ ኩራት እንዳልናደ
እንቢታዊ መልሱን ፣
ያ'ይኾንም ምላሹን ፣ ይዞ ነው የኼደ።

እማምዬ ጀንበር ፣ ደማቅ ፀሓይቱ
የማትጠልቀዋ ፣ እመት አዛኝይቱ
ዐይን ዐይኔን እያየች ፣
ትንንሽ እጆቼን . . .
በእጆቿ ወዘና በቅቤ እያሰላች
እውነትና ምኞት እያሰናሰለች
የመዳፌን መሥመር ማንበቧን ቀጠለች።

ነገኽ እውነት አለው! አንተ ማለት ተስፋ
ረዥሙ ጒዞኽ . . .
ባ'ምላክ እናት ያለ ፣ ታቅፎ ባ'ክናፏ።
ዕንቅፋት ያልበዛው መንገድኽ የቀና
እንደ እጅኽ ለስልሶ ፣ ያርብብ ያ'ንተ ዳና!

( ... አለች ... )

( ... እጇን ያዝኩ ላነበው ... )

የእናቴ መዳፍ .
መንገዱ የበዛ ፣ ሻካራ ሽንትርትር
ምን? ብዬ ላንብበው !
ቍራጭ መሥመር ትርትር።
ከጣቶቿ ግርጌ . .
ፈለግ ነግሦበታል!
ግቻ ሠርቶባታል!
ቀንድ መሰለብኝ የሚያሳሳው ጥፍሯ
ልስላሴው ጠፍቶ . . .
በየአንጓው ሥፍር ፣ እዥ ይዟል መሥመሯ።

( . . የእምዬ መዳፍ . . )

መጻተኛ ኾንኩኝ ልቤ ተሰበረ !
መዳፏ ነገረኝ ውስጤም ተሸበረ!
እናቴ አልማዝ . . .!
መጋቤ ብርሃን ፣ ልትከስም እንደ ሻማ ፤
እመት አዛኚቷ . . .!
ደርቃና ጠውልጋ ፣ ልትረግፍ እንዳ'በባ።
ውብ ጸዳል ዐይኖቿ፣ ፀሓይ የነበሩ
ሞጭሙጨው አነሱ ...
ከ'ርጅና ተጋብተው ፣ ለጊዜ ተዳሩ።
የሐዘን እንባዬ ፣ ፊቴን አረጠበው
ዝሎ! ተሸብሽቦ ፣ ገጼን ዳዋ ዋጠው!)
ዘንግቼው ነበረ! ፣ ፍጻሜ ዘመኑን ፣ እንደነሰነሰ
የድካሟ ካባ ፣ በእናቴ መዳፍ ላይ ፣ እንደተፀነሰ።

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_ሀያ_ሁለት



#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው

መርማሪ ፖሊስ ሚክ ጆንሰን ካርተር በርክሌ ውድ ሽሚዙን በደንብ ማኒኩየር በተሰራው ጣቶቹ በደንብ አድርጎ አስተካከለው:: የዶክተር ሮበርትስ
ታካሚ የሆነው የኢንቨስትመንት ባንከሩ ካርተር በርክሌ ሁሉ ነገሩ ውዷ ነው፡፡ ምርጥ መኖሪያ ቤት፣ ምርጥ ምርጥ የቪንቴጅ ጃንዋር ስፖርት መኪኖች እና ሁሉም ቁጭ ያሉበት በምርጥ ሁኔታ ፈርኒሽድ የተደረገው የቤት ውስጥ ቢሮው እራሱ በጣም ውድ ነው፡፡ እንኳን እቃዎቹ ሲያወራ የሚጠቀምባቸው ቃላቶች ሁሉ በጣም የተመረጡ ናቸው፡፡
እዚህ ቢሮ ውስጥ ቁጭ ብለው እያወሩ እያሉ ካርተር ትላንትና ማታ መኝታ ቤቱ ውስጥ የሆነ ሰው ሊያስፈራራው በማሰብ የሞተ አይጥ አስቀምጦ እንደነበር እየነገረው ነበር። የሞተ አይጥን ማስቀመጣቸው የማፍያዎች ማስፈራሪያ ስልት እንደሆነ ጭምር እያስረዳው ነበር፡፡

“ይሄን ነገር ያደረጉት በእርግጥም እኔን ሊያስፈራሩ አስበው ነው፡፡ደግሞም ተሳክቶላቸዋል። ባይገርምህ መርማሪ ፖሊስ ጆንሰን እናንተ ወደ እኔ ባትመጡ እንኳን እኔ እራሴ ጉዳዩን ለማመልከት ወደ እናንተ መምጣቴ አይቀርም ነበር።

ጆንሰንም ራሱን በአዎንታ በመነቅነቅ የቤቱን ዙሪያ ሲመለከት ዕቃዎቹ
በደንብ ከመወልወልም በላይ የመፅሀፍ መደርደሪያው ሼልፍም ራስን
በመገንባት ላይ እና በፋይናንስ ዙሪያ በተፃፉ መፅሀፍት በሥርዓት
ተጠቅጥቀዋል። አሁን ላይ ካርተር በርክሌይን እየተመለከተው ያለው ጆንሰን
ዶክተር ሮበርትስ ስለ ካርተር ከማስታወሻዋ ላይ ከፃፈችው ነገር ጋር
በመስማማቱ ተናደደ፡፡

ጆንሰን ካርተርን አስመልክታ ኒኪ የፃፈችውን ሲያነብ “መቀወሱ
ያልተረጋገጠ በከንቱ ስሜት ውስጥ የሚናውዝ የሜክሲኮ ወንጀለኞች
ሊገድሉት እንደሚያሳድዱት የሚናገር (ለዚህ ምንም ማረጋገጫ የሌለው)
ለረዥም ጊዜ በጭንቀት ውስጥ የኖረ። ምናልባት በልጅነቱ በደረሰበት ስቃይ
ምክንያት ሊሆን ይችላል? (ወይንም ደግሞ ሜክሲኮ ውስጥ በጉርምስናው
ዘመን ኖሯልና ምናልባት እዚያ የሆነ ነገር ተከስቶ ይሆን?) ውስጡ ያላደገ
ቋሚ የሆነ ፆታዊ ግንኙነት የሌለው እና በግንኙነት አብረውት ያሉ ሰዎችንም በጣም አድርጎ የሚቆጣጠር ነው።” ይላል ማስታወሻው፡፡

ዶክተር ሮበርትስ ካርተር በርክሌን የገለፀችበት መንገድ በሙሉ የተቀበለው ቢሆንም አንድ ነገር ረስታለች እሱም “የሰዎች አትኩሮትን (ታይታን) የሚፈልግ ባህሪ ያለው መሆኑ ነው። ይህንን ደግሞ በእሱ ላይ ያላየችው እሷም የዚህ ልክፍት ስላለባት ነው ብሎ አሰበ፡፡ ለዚህም ነው
ካርተር ከዚህ በፊት በተካሄዱት ግድያዎች ውስጥ ዋነኛ ተፈላጊ ሰው መሆኑን ለማሳየት ያጫወተውን የአይጥ ታሪክ ፈጥሮ ለጆንሰን የተናገረው።


ይሄ ቀሽም ሰው ራሱን እንደተፈላጊ ሰው ያያል ወይንም ደግሞ የሆነ እሱ ስለግድያው የሚያውቀውን ነገር እንዳላውጣጣው እያዘናጋኝ ነው
ብሎም አሰበ፡፡

“ቤትህ ውስጥ ጠባቂዎች አሉህ መሰለኝ?” ብሎ ቅድም ወደ ቤቱ ሲገባ
የተመለከታቸውን ብዙም ስልጠና እንደሌላቸው የሚያስታውቁትን የጥበቃ
ሰዎቹን አልፎ እንደገባ አስታውሶ ካርተርን ጠየቀው። ቤቱ ውስጥ ሲገባ ከጠባቂዎቹ ሌላም የሲ.ሲ.ቲቪ
ካሜራዎችንም አይቶዐካሜራዎችንም በየቦታው ገጥመሃል አይደል እንዴ?”

“አዎን ቤቱ ጥበቃ ስለሚያስፈልገው በጠባቂዎችም፣ በካሜራም ነው
የሚጠበቀው። ግን ዋናው መኝታ ቤቴ ውስጥ ካሜራ አልገጠምኩኝም” ብሎ
መለሰለት፡፡

ጆንሰንም “ለምን ዋናው መኝታ ቤትህ ውስጥ ካሜራ አላስገጠምክም?
ብሎ ጠየቀው፡፡

ባንከሩም እንዴት ይሄ አይገባህም በሚል ሀሳብ ይመስል የጎረምሳ ፈገግታ ከለገሰው በኋላ “እዚህ ጋር የተማረ ሰው ግምት ይኖርሃል ብዬ አስባለሁ። ጠባቂዎቼ ከሁሉም ካሜራዎች በቀጥታ መረጃዎች ይደርሳቸዋል።እኔ ደግሞ በግሌ የማደርጋቸውን ነገሮች ማንም እንዲያውቅብኝ አልፈልግም። ለዚያም ስል ነው በዋናው መኝታ ክፍሌ ውስጥ ካሜራ ያላስገጠምኩት፡፡ በሁሉም ወደ ቤቴ በሚያስገቡ በሮች ላይ ካሜራ
ተገጥሞባቸዋል። እሱ ላይ ብቻ ሳይሆን ፎቅ ላይም ካሜራዎችን
አስገጥሜያለሁ። ስለ እዚህ ወደ እዚህ ቤት የሚገባም ሆነ የሚወጣ ሰው
በካሜራው መታየት ይችላል” ብሎ መለሰ፡፡

“መልካም” አለና ጆንሰን በመቀጠልም “የሞተውን አይጥ መኝታ ቤትህ
ተቀምጦ ካገኘህ በኋላ መቼስ ካሜራዎቹ የቀረፁትን ቪዲዩዎች ተመልክተሀቸዋል አይደል?” ብሎ ጠየቀው፡፡

“አዎን አይቻቸዋለሁ”

“ግን ማንም ሰው አላየህም?”

ቤቴ ውስጥ ከሚሰሩ ሰዎች በስተቀር አንድም ሰውን አላየሁም። ይሄ ታዲያ አይገርምም?” ብሎ የሸሚዙን ኮሌታ በሀይል ጎተተው።

“እና እንዴት ነው ይሄ አንተ የማፍያዎች የማስፈራሪያ መንገድ ነው ብለህ ያሰብከውን የሞተውን አይጥ መኝታ ቤትህ ድረስ ሊያስቀምጡ የቻሉት?” ብሎ ጆንሰን ጠየቀ፡፡

ካርተርም ፊቱ ላይ ግራ የመጋባት ፊት እያሳየው “እኔ ይሄንን በምን አውቃለሁ? መርማሪ ፖሊሱ እንግዲህ አንተ ነህ አይደል? አንተው ንገረኝ
እንጂ” ብሎ መለስ፡፡
“እና ቪድዮው ላይ አዲስ ሰው እስካላየህ ድረስ ቤት ውስጥ የሚሰራ
ሰው ነው አይጡን መኝታ ቤትህ ያስቀመጠው ማለት ነው፡፡ አይመስልህም?”ብሎ ጠየቀው እኔ ጋር አለ ብሎ ባልጠበቀው የራሱ ትዕግስት ጭምር እየተገረመ፡፡

“ይሄማ ሊሆን አይችልም፡፡ ምክንያቱም እኔ እነዚህን ሰዎች ስቀጥር
የበፊት ህይወታቸውን በሚገባ አስጠንቼ እና ተጠንቅቄ ነው፡፡ ስለሆነም
አሁን አንተ የተናገርከው ነገር ሊሆን አይችልም...”

ብሎ ያሰበውን ነገር ተናግሮ ሳይጨርስ ጆንሰን አቋረጠው እና ምናልባት አይጡን ልታሳየኝ ትችላለህ? ስለዚህ አይጡን አንስቼ ምርመራ እንዲደረግበት ማድረግ እችላለሁ” አለው ከወንበሩ ላይ ተነሳ፡፡
“አይጡን ላሳይህ አልችልም” ብሎ መለሰለት፡፡ ጆንሰንም የካርተርን
መልስ ሲሰማ ዶክተር ሮበርትስ “ዝም ብሎ የቅዠት ሀሳብ የሚፈጥር ብላ
የተናገረችው ነገር ትክክል እንደሆነ አወቀ።

ለምንድነው አይጡን የማታሳየኝ?” ብሎ ኮስተር ብሎ ጠየቀው እና ለእንደዚህ አይነት ሰው ዶክተር ሮበርትስ እንዴት በየቀኑ የቴራፒስት ህክምና ልትሰጥ እንደምትችል ራሱን ጠየቀ፡፡ እንደዚህ አይነቶቹ ቴራፒስቶች አፍንጫቸው መመታት የለበትም ታዲያ?

“ትላንትና ማታ ነው አይጡን ያገኘሁት እሱን ደግሞ ነግሬሀለሁ አይደል?” ብሎ ካርተር ክርክሩን በመቀጠል “ቤቴን የምታፀዳው ሴት ደግሞ እስከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ድረስ አልመጣችም ነበር፡፡ እሷ እስክትመጣ ድረስ ደግሞ አይጡን ክፍሌ ውስጥ ልተወው አልችልም፡፡ ምክንያቱም አይጡ ምን አይነት በሽታ ይዞ እንደመጣ ማንም አያውቅም፡፡” ብሎ መለሰለት።

“እና መረጃ የሚሆነንን ነገር ነው የጣልከው?”

“መጣል ነበረብኝ”

“አይጡን ከክፍልህ ስታስወግድ ያየህ ሰው አለ?”

የለም ያው እንዳልኩህ በጣም መሽቶ ነበር” ብሎ ሲመልስለት የጆንሰን
ትዕግስት ተሟጥጦ ስላለቀ አሁንም ከተቀመጠበት ወንበር ላይ ተነሳ፡፡
የታለ ቆሻሻ የምትጥልበት የቆሻሻ ማስቀመጫህ? ምናልባት አይጡ
እዚያው ቆሻሻ መጣያው ውስጥ ይኖር ይሆናል ይሄኔ” አለው ጆንሰን
ይህንን የጆንሰን ጥያቄ ሲሰማ ቢያንስ ካርተር ማፈር ነበረበት፤ ግን እሱ
ይበልጥ ድርቅ ብሎ “አሁን ላይ በእርግጠኝነት ባዶ ነው የሚሆኑት። ቆሻሻ የሚሰበስቡ ሰዎች ዛሬ በጠዋት ነው ያለወትሮ የመጡት። ያንን አስቢ
አይጡን ሌላ ቦታ ማስቀመጥ ነበረብኝ፡፡ ወይም በጣም ነው ያጠፋሁት.”ጆንሰን ወደ ዋናው የፖሊስ ማዘዣ ጣቢያ ለመመለስ መኪናውን በተጨናነቀ መንገድ ላይ ሲያሽከረክር ከአንድ ሰዓት በላይ ፈጅቶበታል ጣቢያውም የደረሰው በሚያስጠላ
👍2
ስሜት ውስጥ ሆኖ ነበር፡፡ ምክንያቱም ካርተርን ያገኘው በዶክተሯ ማስታወሻ ላይ እንደተገለፀው ያልተረጋጋ
አዕምሮ ያለው ሰው ሆኖ ነው። በዚያ ላይ ደግሞ ካርተር ሊዛን አይቷት አያውቅም፡፡ ከትሬይም ጋር የቀረበ ግንኙነት የላቸውም፤ እናም ደግሞ የተጠርጣሪያቸውን ብራንዶን ግሮልሽ የሚል ስምን ለአንድም ቀን ቢሆን
ሰምቶት እንደማያውቅ ነው የተገነዘበው፡፡ ብቻ በአጠቃላይ ባንከሩ ከዚህ
ወንጀል ጋር የተያያዘ አንድም ነገር እንደሌለው ለመረዳት በመቻሉ ካርተርን
ማግኘቱ ውድ ጊዜውን እንዳጠፋበት ብቻ ነው ያወቀው፡፡

የዋናው ማዘዣ ጣቢያ ህንፃ ውስጥ ገና እንደገባም ነበር ዋናው አዛዥ ሊያናግራቸው እንደሚፈልጓቸው ጉድማን የነገረው።

“እኮ ኣሁን?”

“አዎን አሁኑኑ” ብሎ ጉድማን የእጁን ሰዓት ከተመለከተ በኋላም

“እንዲያውም በማርፈድህ ተናድዶብሃል”
“እንዴ እኔ እንዴት ነው ያረፈድኩት?” ብሎ ጆንሰን ተቃወመው እና
“አሁን አይደል እንዴ ሊሰበስበን የጠራን? እኔ ጠዋት 1፡30 ላይ ቢሮገብቼ ነበር በክርስቶስ! እንዲያውም አንተ የት ነበርክ ያኔ?”

“ይቅርታ” ብሎ ጉድማን አጉረመረመ እና በመቀጠልም “ማታ የሆነ ነገር
ገጥሞኝ ስለነበር አርፍጄ ነው የተኛሁት።”
ጠዋት ላይ ጉድማን አልጋው ላይ ተኝቶ እያለ የትላንት ማታውን ከኒኪ ሮበርትስ ጋር ያሳለፈውን ምሽት እያሰበ ከዞረ ድምሩ ጋር ሲታገል ነበር።

ለስላሳ እና ሙቅ ገላዋን እንደፈለገው እያደረገ እንዲያድር ፈቅዳለት ነበር
እኮ፡፡ ግን ምርመራዬን ያበላሽብኛል ብሎ ነው ከእሷ ጋር ማደሩን የተወው።

“ጉድማን! ጆንሰን! ዛሬ የላችሁም እንዴ” ብሎ ዋናው የጣቢያ አዛዥ ብሩዲ እንደብራቅ ሲጮህ ድምፁ በገደል ማሚቶ እያተስተጋባ አዳራዃን
አልፎ የጉድማንን ጆሮ ሰነጠቀው።

“አቤት ጌታዬ!” ብለው የአዛዡ ቢሮ ውስጥ ገብተው ወንበር ስበው
ተቀመጡ።

“እሺ! እስቲ ስለምርምራችሁ አሳውቁኝ” አላቸው ብሩዲ፡፡

ብሩዲ ግዙፍ ሲሆን ዕድሜው በስልሳዎቹ መጀመሪያ ላይ ይገኛል፡፡
በጣም በቶሎ የሚናደድ ከመሆኑም በላይ ሁልጊዜም ጨፍጋጋ ስሜት
የሚታይበት ሰው ነው፡፡

“ሁለት ተቆራርጠው የተገደሉ ሰዎች አሉን፡፡ ሰዎቹን የገደለውን ሰው
ወይንም ቢያንስ ተጠርጣሪው እንኳን አልተያዘም፡፡ አንዲት የታወቀች
ሳይካትሪስትም የግድያ ሙከራ ተደርጎበታል፡፡ ከተገደሉት መካከል አንዷ
ደግሞ የእሷ ታካሚና የቢሊየነር ቅምጥ የነበረችው ሴት ናት፡፡ ይህንን ነገር
ሚዲያዎች እንደ ጉድ እያራገቡት ይገኛሉ።” አላቸው በቁጣ ተሞልቶ
ሁለቱም ላይ እያፈጠጠ።

“አዎን ጌታዬ” አለ ጉድማን መሬት መሬቱን እያየ፡፡

“ግን ደግሞ ነገሩ እየባሰ እንጂ እየቀዘቀዘ አልሄደም።” አለ እና በቁጣ ጦዘ፡፡ ቀጠለናም “ደግሞ በኢንተርኔት ዞምቢው ገዳይ በሚል ርዕስ የገዳዩን ሰው ዜና እያራገቡት ይገኛሉ። እሱ እሺ ይሁን ዛሬ ደግሞ ጭራሽ ኤን.ቢ.ሲ 4 የቴሌቭዥን ጣቢያ ስለዚህ ዞምቢ ገዳይ የሚባል የማይረባ ነገር ጠዋት ላይ ሲዘግብ ነበር፡፡ ምንድነው በመስራት ላይ ያላችሁት?” ብሎ አሁንም
በቁጣ ስሜት ውስጥ እንደሆነ ጠየቃቸው፡፡

“ምናልባት ጉዳዩ ያፈተለከው ከሬሳ ምርመራው ሆስፒታል ሊሆን
ይችላል” ብሎ ጆንሰን መለሰ፡፡

“ዜናው ከየትም ቦታ አፈትልኮ ቢወጣ እኔ ግድ አለኝ ታዲያ?!” ብሎ ብሩዲ ይበልጥ በቁጣ ነበልባል እየነደደ ጠየቃቸው፡፡

ጆንሰንም በመቀጠል “የሬሳ መርማሪዋ ጄኔ ፎይሌ የተፋቀ የቆዳ ህዋስን
በመጀመሪያዋ ሟች ጥፍር ውስጥ አገኘች፡፡ ይህ ህዋስም በሁለተኛው ሟች
ላይ ከተገኘው የፀጉር ዲኤንኤ ጋር አንድ አይነት ሆነ፡፡ የቆዳ ህዋሱም ሆነ
ፀጉሩ የአንድ ብራንዶን ግሮልሽ የሚባል ከቤቱ የጠፋ ሰው መሆኑም ተረጋግጧል። ይህ ነገር ነው አፈትልኮ የወጣው እና በየኢንተርኔቶች ላይ
የተሰራጨው” ብሎ ጆንሰን አብራራ፡፡
ቺፍ ብሩዲም በረዥሙ ተነፈሰና “እና አሁን አንተ የምትነግረኝ ያለኸው
ዋነኛው በግድያው ላይ ተጠርጣሪ የሆነው ግለሰብ እንደሞተ ነው ማለት
ነው?” ይሄኔም ጉድማን ጣልቃ ገብቶ

“ብራንዶን ግሮልሽን ዋነኛ ተጠርጣሪያችን አድርገን አልያዝነውም። እሱ አደንዛዥ ዕፅ በብዛት በመውሰድ የተነሳ የዛሬ ስምንት ወር ህይወቱ አልፏል። ግድያዎቹን የፈፀመው ወንጀለኛም በሆነ መልኩ የብራንዶንን
ዲ.ኤን.ኤ በገደላቸው ሰዎች ላይ ሲያስቀምጥ ነበር፡፡ ይህንንም የሚያደርገው ብራንዶን ግሮልሽ እንደሞተ ስለሚታወቅ በግድያዎች ላይ ምርመራ
እንዳይደረግ ለማድረግ ነው” ብሎ ጉድማን አብራራ፡፡

“ይህ አንደኛው ቲዎሪያችን ነው” ብሎ ጆንሰን አልጎመጎመ::

“እሺ ሌላኛው ግምታችሁስ?” ብሎ ብሩዲ ጠየቃቸው፡፡

ብሩዲም አይኑን ከእነርሱ ላይ ሳይነቅል “ይሄኛው ግምታችሁ መቼስ ዞምቢ ምናምን የሚባል ነገር የለውም?”

“የለውም ጌታዬ” ብሎ ጆንሰን ጉሮሮውን ካጠራ በኋላ “ይሄኛው ግምታችን የሚያነጣጥረው ራሷን ዶክተር ኒኪ ሮበርትስን ማእከል በማድረግ ነው” ብሎ ሲናገር ጉድማን አይኑን በቁጣ ቢያጉረጠርጥበትም ጆንሰን ግን
ችላ ብሎት ነገሩን ማብራራቱን ቀጠለ፡፡

“መርማሪ ፖሊስ ጉድማን እና እኔ ለአራት ቀናት ያህል በታካሚዎቿ ላይ የፃፈቻቸውን ማስታወሻዎች ስናገላብጥ እና አንድ አንድ ታካሚዎቿንም ለማናገር ችለን ነበር። ሁለታችንም ግድያው የደረሰባቸው ግለሰቦች ከዶክተሯ ጋር ግንኙነት ያላቸው መሆናቸውን ለማወቅ ችለናል። እንዲያውም ጉድማን እራሷ ዶክተሯ የገዳዩ ዋነኛ ዒላማ እንደነበረች ያምናል” ብሎ ተናገረ፡፡

ዋና አዛዥ ብሩዲም አይኑን አጥብቦ ጆንሰንን እየተመለከተው “ግን አንተ
በዚህ ጉዳይ ላይ አትስማማም?” ብሎ ጠየቀው፡፡

“አዎን በባልደረባዬ ሀሳብ አልስማማም ጌታዬ! ምክንያቱም ዶክተሯ በመጀመሪያዋ ሟች በሊዛ ፍላንገን ላይ የፃፈቻቸው ማስታወሻዎች ጤናማ
አይደሉም። ሊዛ ፍላንገን ከባለትዳር ጋር ያላትን ወሲባዊ ግኑኝነት እንደማትወደው፣ ከቢሊየነሩ ያረገዘችውን ልጅ በማስወረዷም በጣም
እንደተበሳጨችባት እና ሊዛ የምትወስደውን ዕፅም ወዳው እየወሰደችው መሆኑን በሚገልፅ መልኩ ነበር ነበር ማስታወሻዎቹን የፃፈፈችው እኔ
እንደማምነው አንድ በስነ ልቦና ህክምና ላይ የተሰማራ ባለሙያ በሽተኞቹን
ማከም እንጂ ስለ በሽተኞቹ ፍርድ መስጠት አይጠበቅበትም ብዬ አስባለሁ።

በሟቿ ላይ የተፃፉት ማስታወሻዎች በሙሉ በበሽታዋ ላይ ፍርድን የሚሰጥ
ሆነው ከመገኘታቸውም በላይ በጣም በንዴት የተሞሉ አስተያየቶች ነበሩ።”
ብሎ ጆንሰን ተናግሮ ጨረሰ፡፡....

ይቀጥላል