#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
..“ይሸጣል እንዴ?” ከመካከላቸው አንዱ፡፡
“አሉልህ እኮ አሁን ወጣ ብለን ብንፈልግ ደማቸውን እንደ ጭማቂ ለመሸጥ የሚንጐራደዱ አይታጡም" ”ሌላው፡፡ ይሄ ደግሞ የገንዘብ መስዋዕትነትን ጠየቀ፡፡ አሁንም ተፋጠጡ፡፡
“አቦ ትጠራ ምን ትሆናለች” ባዩ በዛና ትህትና ይሄንን መርዶ በጠዋቱ እንድትረዳ ፈረዱባት፡፡ ከዚያም ልጁ ሊጠራት እየበረረ ከሆስፒታሉ ወጣ፡፡
እሷ በዚያን ሰዓት አገር ሠላም ነው ብላ ለእናቷ የምትወስደውን ምግብ እያዘጋጀች ነበር፡፡ ወንድሟ ለሷ ለሚወዳት እህቱ ብሎ በዚህች
ስዓት በሕይወትና በሞት መካከል ይገኛል፡፡
በጠዋቱ የተንኳኳውን በር ሄዳ ከፈተች፡፡ ለምን እንደሆነ አላወቀችም ልቧ ሽብር ሽብር አለባት፡፡
“አንዱአለም ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ገብቷል” አላት ጭክን ብሎ።
“ኡ ይ!” ምን ሆኖ!” ጮኸች።
“ሰው ደብድቦት፡፡ አሁን በአስቸኳይ ደም ተጠይቋል” ቁርጡን ነገራት። ከዚያ በኋላ ያደረገችውን አታውቅም፡፡ የሞተ ነው የመሰላት፡፡
የውጭውን በር በርግዳ....
“ኡኡ.... አንዱዬ ...! አንዱዬ....! ወንድሜን!... ወንድሜን!”
ሩጫዋን ቀጠለች። ልጁም ከኋላ ከኋላዋ እየተከተለ ተያይዘው ቁልቁል ይሮጡ ጀመር፡፡ እንደዚያ ራሷን ስታ እየጮኸች ስትሮጥ የሚያያት ሰው በጣም ነበር ያዘነላት፡፡ እንባዋ እንደጉድ ይፈሳል፡፡
ከጥቁር አንበሳ ት/ቤት ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ለመሻገር ከላይም ከታችም መኪና ማየት ሲገባት፤ እንደዚሁ ግብኗን እየበረረች ግማሹን አስፋልት ተሻግራ ደሴቱን አቋረጠችና ወደ ሁለተኛው አስፋልት ጥልቅ ብላ ገባች፡፡
ከዚያ ከላይ ከቴዎድሮስ አደባባይ ቁልቁል እየበረረች የምትመጣው ውይይት ታክሲ በድንገት ጥልቅ ብላ የገባችውን ልጅ ለማዳን ሹፌሩ ፍሬኑን በሃይል ሲረግጠው፤ መኪናዋ ወደጐን ዞረችና ደሴቱ መሐል ገብታ ተቀረቀረች፡፡
እዚያ ታክሲ ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች በድንጋጤ ውሃ ሆነዋል፡፡ ትህትና የዚህ ሁሉ መንስኤ እሷ መሆኗን አታውቅም፡፡
ሩጫዋን አላቆመችም፡፡ ልጁ በተፈጠረው አደጋ ተደናግጦ ጭንቅላቱን
በሁለት እጆቹ ይዞ ቀረ፡፡ ከዚያም ሮጦ ደረሰባትና! እጇን ይዞ ይማፀናት
ጀመር፡፡ አልሰማ አለችው፡፡ ያለው አማራጭ ከኋላ ከኋላዋ መሮጥ ብቻ
ነበር፡፡ ተያይዘው ሆስፒታል እንደ ደረሱ፤ እነዚያ የሆያ ሆዬ ጓደኞቹ ተሰባስበው! ተቀበሏት፡፡
“የት ነው ያለው? ወንድሜ የት ነው? አንዱዬ የታለ? ሞቶ እንደሆን ንገሩኝ” ትለፈልፋለች፡፡ ከስንት ልመና በኋላ እንደምንም ብለው ሊያረጋጓት ሞከሩ፡፡ ከዚያም ሀኪሞች “አይዞሽ ደህና ነው” ብለው ካጽናኗት በኋላ ደም እንድትሰጥ ተደረገ፡፡
“ወንድሜን ዐይኑን ልየው እባካችሁ?” እያለች ፤ እያለቀሰች ብትለምንም “ሪከቨሪ” ስለሆነ መግባት አይቻልም ተባለች፡፡
ቀስ በቀስ ነፍሷን መግዛት ስትጀምር፤
ለአዜብ ስልክ አስደወለችላትና አዜብ መጣች፡፡ አዜብ ሁኔታውን እንዳረጋገጠች...
“ምን መዘዘኛ ነኝ?” የሚል መጥፎ ስሜት ተሰማት፡፡ ሚስጥሩን ስትነግረው በፍፁም የዚህ አይነቱ አደጋ ይደርስበታል ብላ አልገመተችም ነበር። ትንሽ እዚያ አካባቢ ዞር፤ ዞር፤ እያለች ከቆየች በኋላ፤ ሹልክ ብላ ሳትነግራት ወደ ቤቷ ሄደች፡፡
ትህትና ጨንቋት፤ አጽናኝ በምትፈልግበት ሰዓት ላይ ጓደኛዋን ብትፈልግ አጣቻት፡፡ ወዲያና ወዲህ ተዘዋወረች፡፡ ተዟዟረች፡፡ አዜብ ግን የለችም፡፡ በመጨረሻ ላይ እቤት ስልክ ደወለች፡፡ “የለችም” አስባለች፡፡ እየመሸ መጣ፡፡ እንደገና ስልክ ደወለች፡፡ አሁንም የለችም ተባለች፡፡
ክው ብላ ደነገጠች፡፡ “ምነው? ምን አደረኳት አዜቢናን?” ሽምቅቅ ብላ፤ ስልኩን አስቀምጣ፤ ብቻዋን ጭር ያለ ቦታ ፈልጋ ተቀመጠችና፤ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች፡፡ እናቷ የካቲት አስራ ሁለት
ሆስፒታል፣ ወንድሟ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል፣ ምን ዓይነት ስቃይ
ነው? እንደተመኘችው ሳታየው መሸ፡፡ በማግስቱ እናቷን ጠይቃ፤ ወደ
ወንድሟ መጣች፡፡ ልታየው አልቻለችም፡፡ ፀጉሯን እንኳን ማበጠር አቁማለች፡፡ እንደዚያ የምታምረው ልጅ ነገሮች ተደራርበውባት፧ ማስፈራሪያ እየመሰለች ነው፡፡ እንደዚህ ሆና መከራዋን ካየች በኋላ ወንድሟን ያገኘችው፤ በሶስተኛው ቀኑ ነው፡፡
አንዱአለም ድንበሩ ከሞት ድንበር ደርሶ ተመለሰ፡፡ በሶስተኛው ቀን፤ በሶስተኛ ማዕረግ ከቀዶ ጥገና በሽተኞች ጋር ተቀላቀለ፡፡ እንደዚያ ፊቱ አብጦና፤ ጠቁሮ፤ ስታየው የምትሆነውን ነበር ያጣችው፡፡
“አንዱዬ ምንድነው የሆንከው?” ቀስ ብላ ጠየቀችው። ከትንፋሹ
ጋር እየታገለ....
“እንደሻው... አስደበደበኝ” ብሉ ነገራት፡፡ በዚህ ጊዜ የተሰማትን ስሜት መግለጽ ያስቸግራል፡፡ አዜብ የሸሸችበት ሚስጥር አሁን ገና ወለል ብሎ ታያት፡፡ ሰውነቷን የሆነ ነገር ውርር አደረጋት :: እንደሻው
በግንባሩ ላይ ብዙ ጠመዝማዛ ቀንዶች አብቅሎ፣ ጥርሶቹ ተስለውና፤
አንደመጋዝ ሾለው፣ ጥፍሮቹ እንደ ጃርት እሾህ ተንጨፍርረው፣ ታይዋት፡፡ .
እንደሻው ... እንደሻው ... እንደሻው ... አእምሮዋን እንድትስት አድርጉ ከመታት በኋላ ሊከመርባት፤ በሀሳብዋ መጣባት፡፡ ሰውነቷ እንደሻው ምን ያላደረጋት ነገር አለ? የምትወደው ሻምበል ብሩክን ያጣችው በእንደሻው ምክንያት ነው፡፡ ዶክተር ባይከዳኝ እንደዚያ ውሻ አድርጐ የሰደባት፤ በኋላም ስለእናቷ ክፉ ንግግር የተናገራት፤ እንደሻው በፈጸመባት ወንጀል ምክንያት ነው፡፡ ስራዋንም ያጣችው በሱ
ድርጊት የተነሳ ነው፡፡ ለዚህ ሁሉ ግፍ ምንም የበቀል እርምጃ አልወሰደችም፡፡ እሷ ብትተወውም ግን እሱ ሊተዋት አልፈለገም፡፡
ይሄውና አሁን ደግሞ እንደ ዐይኗ ብሌን የምትሳሳለት፤ አንድና ብቸኛ ወንድሟን እንዳይሞት እንዳይድን፣ አድርጉ! አስደበደበው፡፡ ግን ለምን ይሄን ያክል ጨከነባት?
“የሰው ልጅ አይደለሁም እንዴ? ምነው ምን አደረኩት?” በሚል ጭንቀት ተውጣ ራሷን ጠየቀች፡፡ በሷ እምነት ምንም
አላደረገችውም።የፈጸመችበት በደል አልነበረም፡፡ የማፈቅረው ሰው ስላለኝ
ይቅርታ አድርግልኝ ብላ ለምና ተለማምጣ ልታግባባው ሞከረች እንጂ
አንዳችም ክፉ ነገር አልወጣትም፡፡እሱ ግን ያንን እንደ ጥቃት ቆጥሮ፤ በጭካኔ ደብድቦ፧ ክብረ ንጽህናዋን መድፈሩ ሳያንሰው አሁን ደግሞ እንደገና ,በወንድሟ ላይ የጭካኔ በትሩን አሳረፈ፡፡ግን ለምን?... ለምን?...ለምን?... ለዚህ ጥያቄዋ መልሱ ብዙም ሳይቆይ ወደ አእምሮዋ መጣላት፡፡ አላንገራገረችም፡፡ ይሄ የመጨረሻው ምዕራፍ ነው ስትል ወሰነች፡፡ የሆነውን ሁሉ በተቆራረጠ ድምጽ ነገራት፡፡
አሁን ሁሉንም ነገር ሰምታ ከጨረሰች በኋላ አዜብ አሳዘነቻት፡፡ እሷን ጠልታ ሳይሆን፤ በሷ ላይ በተደጋጋሚ ለሚደርሰው አስጠሊታ አጋጣሚ ሁሉ እጂ ስላለበት፤ መጥፎ ስሜት ተሰምቷት እንደሆነ ስታውቅ፤ “ጓደኛዬን አስጨነኳት፡፡ ጭንቀቴ እንጂ አንድም ቀን ደስታዬ
ተርፏት አያውቅም፡፡ በዚያው ለሷም ግልግል ነው፡፡” የሚል ስሜት
አደረባት፡፡
ታሪኩን በሙሉ አንድ በአንድ ሰምታ ስታበቃም፤ አሞቷ ኮስተር አለ፡፡ ለሁሉም ገደብ አለው፡፡ ትዕግሥትም ልክ አለው፡፡ እንኳንስ በደል፤ ማርም ሲበዛ ይመራል። በደል ሲደጋገም ደግሞ ከምሬት በላይ ነው፡፡ በቃ! እንደሻውን ልትበቀለው ስመ እግዚአብሔርን ጠርታ በልቧ መሀላ
ፈጸመች፡፡
አንዱዓለም የምትወደው ታናሽ ወንድሟ፤ የተፈጸመባት ግፍ አንገብግቦት ሊበቀልላት ሄዶ ጉድ ሆኗል፡፡ እሷ ደግሞ በታናሽ ወንድሟ ላይ ለተፈጸመው ወንጀል ምላሽ መስጠት አያቅታትም፡የመጨረሻው የአባቷ ቅርስ ታያት፡፡ በክብር ተሸፍኖ በሣጥን ውስጥ በድብቅ
የተቀመጠውን፣ እሷና እናቷ ብቻ የሚያውቁትን፣ መቶ አለቃ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
..“ይሸጣል እንዴ?” ከመካከላቸው አንዱ፡፡
“አሉልህ እኮ አሁን ወጣ ብለን ብንፈልግ ደማቸውን እንደ ጭማቂ ለመሸጥ የሚንጐራደዱ አይታጡም" ”ሌላው፡፡ ይሄ ደግሞ የገንዘብ መስዋዕትነትን ጠየቀ፡፡ አሁንም ተፋጠጡ፡፡
“አቦ ትጠራ ምን ትሆናለች” ባዩ በዛና ትህትና ይሄንን መርዶ በጠዋቱ እንድትረዳ ፈረዱባት፡፡ ከዚያም ልጁ ሊጠራት እየበረረ ከሆስፒታሉ ወጣ፡፡
እሷ በዚያን ሰዓት አገር ሠላም ነው ብላ ለእናቷ የምትወስደውን ምግብ እያዘጋጀች ነበር፡፡ ወንድሟ ለሷ ለሚወዳት እህቱ ብሎ በዚህች
ስዓት በሕይወትና በሞት መካከል ይገኛል፡፡
በጠዋቱ የተንኳኳውን በር ሄዳ ከፈተች፡፡ ለምን እንደሆነ አላወቀችም ልቧ ሽብር ሽብር አለባት፡፡
“አንዱአለም ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ገብቷል” አላት ጭክን ብሎ።
“ኡ ይ!” ምን ሆኖ!” ጮኸች።
“ሰው ደብድቦት፡፡ አሁን በአስቸኳይ ደም ተጠይቋል” ቁርጡን ነገራት። ከዚያ በኋላ ያደረገችውን አታውቅም፡፡ የሞተ ነው የመሰላት፡፡
የውጭውን በር በርግዳ....
“ኡኡ.... አንዱዬ ...! አንዱዬ....! ወንድሜን!... ወንድሜን!”
ሩጫዋን ቀጠለች። ልጁም ከኋላ ከኋላዋ እየተከተለ ተያይዘው ቁልቁል ይሮጡ ጀመር፡፡ እንደዚያ ራሷን ስታ እየጮኸች ስትሮጥ የሚያያት ሰው በጣም ነበር ያዘነላት፡፡ እንባዋ እንደጉድ ይፈሳል፡፡
ከጥቁር አንበሳ ት/ቤት ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ለመሻገር ከላይም ከታችም መኪና ማየት ሲገባት፤ እንደዚሁ ግብኗን እየበረረች ግማሹን አስፋልት ተሻግራ ደሴቱን አቋረጠችና ወደ ሁለተኛው አስፋልት ጥልቅ ብላ ገባች፡፡
ከዚያ ከላይ ከቴዎድሮስ አደባባይ ቁልቁል እየበረረች የምትመጣው ውይይት ታክሲ በድንገት ጥልቅ ብላ የገባችውን ልጅ ለማዳን ሹፌሩ ፍሬኑን በሃይል ሲረግጠው፤ መኪናዋ ወደጐን ዞረችና ደሴቱ መሐል ገብታ ተቀረቀረች፡፡
እዚያ ታክሲ ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች በድንጋጤ ውሃ ሆነዋል፡፡ ትህትና የዚህ ሁሉ መንስኤ እሷ መሆኗን አታውቅም፡፡
ሩጫዋን አላቆመችም፡፡ ልጁ በተፈጠረው አደጋ ተደናግጦ ጭንቅላቱን
በሁለት እጆቹ ይዞ ቀረ፡፡ ከዚያም ሮጦ ደረሰባትና! እጇን ይዞ ይማፀናት
ጀመር፡፡ አልሰማ አለችው፡፡ ያለው አማራጭ ከኋላ ከኋላዋ መሮጥ ብቻ
ነበር፡፡ ተያይዘው ሆስፒታል እንደ ደረሱ፤ እነዚያ የሆያ ሆዬ ጓደኞቹ ተሰባስበው! ተቀበሏት፡፡
“የት ነው ያለው? ወንድሜ የት ነው? አንዱዬ የታለ? ሞቶ እንደሆን ንገሩኝ” ትለፈልፋለች፡፡ ከስንት ልመና በኋላ እንደምንም ብለው ሊያረጋጓት ሞከሩ፡፡ ከዚያም ሀኪሞች “አይዞሽ ደህና ነው” ብለው ካጽናኗት በኋላ ደም እንድትሰጥ ተደረገ፡፡
“ወንድሜን ዐይኑን ልየው እባካችሁ?” እያለች ፤ እያለቀሰች ብትለምንም “ሪከቨሪ” ስለሆነ መግባት አይቻልም ተባለች፡፡
ቀስ በቀስ ነፍሷን መግዛት ስትጀምር፤
ለአዜብ ስልክ አስደወለችላትና አዜብ መጣች፡፡ አዜብ ሁኔታውን እንዳረጋገጠች...
“ምን መዘዘኛ ነኝ?” የሚል መጥፎ ስሜት ተሰማት፡፡ ሚስጥሩን ስትነግረው በፍፁም የዚህ አይነቱ አደጋ ይደርስበታል ብላ አልገመተችም ነበር። ትንሽ እዚያ አካባቢ ዞር፤ ዞር፤ እያለች ከቆየች በኋላ፤ ሹልክ ብላ ሳትነግራት ወደ ቤቷ ሄደች፡፡
ትህትና ጨንቋት፤ አጽናኝ በምትፈልግበት ሰዓት ላይ ጓደኛዋን ብትፈልግ አጣቻት፡፡ ወዲያና ወዲህ ተዘዋወረች፡፡ ተዟዟረች፡፡ አዜብ ግን የለችም፡፡ በመጨረሻ ላይ እቤት ስልክ ደወለች፡፡ “የለችም” አስባለች፡፡ እየመሸ መጣ፡፡ እንደገና ስልክ ደወለች፡፡ አሁንም የለችም ተባለች፡፡
ክው ብላ ደነገጠች፡፡ “ምነው? ምን አደረኳት አዜቢናን?” ሽምቅቅ ብላ፤ ስልኩን አስቀምጣ፤ ብቻዋን ጭር ያለ ቦታ ፈልጋ ተቀመጠችና፤ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች፡፡ እናቷ የካቲት አስራ ሁለት
ሆስፒታል፣ ወንድሟ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል፣ ምን ዓይነት ስቃይ
ነው? እንደተመኘችው ሳታየው መሸ፡፡ በማግስቱ እናቷን ጠይቃ፤ ወደ
ወንድሟ መጣች፡፡ ልታየው አልቻለችም፡፡ ፀጉሯን እንኳን ማበጠር አቁማለች፡፡ እንደዚያ የምታምረው ልጅ ነገሮች ተደራርበውባት፧ ማስፈራሪያ እየመሰለች ነው፡፡ እንደዚህ ሆና መከራዋን ካየች በኋላ ወንድሟን ያገኘችው፤ በሶስተኛው ቀኑ ነው፡፡
አንዱአለም ድንበሩ ከሞት ድንበር ደርሶ ተመለሰ፡፡ በሶስተኛው ቀን፤ በሶስተኛ ማዕረግ ከቀዶ ጥገና በሽተኞች ጋር ተቀላቀለ፡፡ እንደዚያ ፊቱ አብጦና፤ ጠቁሮ፤ ስታየው የምትሆነውን ነበር ያጣችው፡፡
“አንዱዬ ምንድነው የሆንከው?” ቀስ ብላ ጠየቀችው። ከትንፋሹ
ጋር እየታገለ....
“እንደሻው... አስደበደበኝ” ብሉ ነገራት፡፡ በዚህ ጊዜ የተሰማትን ስሜት መግለጽ ያስቸግራል፡፡ አዜብ የሸሸችበት ሚስጥር አሁን ገና ወለል ብሎ ታያት፡፡ ሰውነቷን የሆነ ነገር ውርር አደረጋት :: እንደሻው
በግንባሩ ላይ ብዙ ጠመዝማዛ ቀንዶች አብቅሎ፣ ጥርሶቹ ተስለውና፤
አንደመጋዝ ሾለው፣ ጥፍሮቹ እንደ ጃርት እሾህ ተንጨፍርረው፣ ታይዋት፡፡ .
እንደሻው ... እንደሻው ... እንደሻው ... አእምሮዋን እንድትስት አድርጉ ከመታት በኋላ ሊከመርባት፤ በሀሳብዋ መጣባት፡፡ ሰውነቷ እንደሻው ምን ያላደረጋት ነገር አለ? የምትወደው ሻምበል ብሩክን ያጣችው በእንደሻው ምክንያት ነው፡፡ ዶክተር ባይከዳኝ እንደዚያ ውሻ አድርጐ የሰደባት፤ በኋላም ስለእናቷ ክፉ ንግግር የተናገራት፤ እንደሻው በፈጸመባት ወንጀል ምክንያት ነው፡፡ ስራዋንም ያጣችው በሱ
ድርጊት የተነሳ ነው፡፡ ለዚህ ሁሉ ግፍ ምንም የበቀል እርምጃ አልወሰደችም፡፡ እሷ ብትተወውም ግን እሱ ሊተዋት አልፈለገም፡፡
ይሄውና አሁን ደግሞ እንደ ዐይኗ ብሌን የምትሳሳለት፤ አንድና ብቸኛ ወንድሟን እንዳይሞት እንዳይድን፣ አድርጉ! አስደበደበው፡፡ ግን ለምን ይሄን ያክል ጨከነባት?
“የሰው ልጅ አይደለሁም እንዴ? ምነው ምን አደረኩት?” በሚል ጭንቀት ተውጣ ራሷን ጠየቀች፡፡ በሷ እምነት ምንም
አላደረገችውም።የፈጸመችበት በደል አልነበረም፡፡ የማፈቅረው ሰው ስላለኝ
ይቅርታ አድርግልኝ ብላ ለምና ተለማምጣ ልታግባባው ሞከረች እንጂ
አንዳችም ክፉ ነገር አልወጣትም፡፡እሱ ግን ያንን እንደ ጥቃት ቆጥሮ፤ በጭካኔ ደብድቦ፧ ክብረ ንጽህናዋን መድፈሩ ሳያንሰው አሁን ደግሞ እንደገና ,በወንድሟ ላይ የጭካኔ በትሩን አሳረፈ፡፡ግን ለምን?... ለምን?...ለምን?... ለዚህ ጥያቄዋ መልሱ ብዙም ሳይቆይ ወደ አእምሮዋ መጣላት፡፡ አላንገራገረችም፡፡ ይሄ የመጨረሻው ምዕራፍ ነው ስትል ወሰነች፡፡ የሆነውን ሁሉ በተቆራረጠ ድምጽ ነገራት፡፡
አሁን ሁሉንም ነገር ሰምታ ከጨረሰች በኋላ አዜብ አሳዘነቻት፡፡ እሷን ጠልታ ሳይሆን፤ በሷ ላይ በተደጋጋሚ ለሚደርሰው አስጠሊታ አጋጣሚ ሁሉ እጂ ስላለበት፤ መጥፎ ስሜት ተሰምቷት እንደሆነ ስታውቅ፤ “ጓደኛዬን አስጨነኳት፡፡ ጭንቀቴ እንጂ አንድም ቀን ደስታዬ
ተርፏት አያውቅም፡፡ በዚያው ለሷም ግልግል ነው፡፡” የሚል ስሜት
አደረባት፡፡
ታሪኩን በሙሉ አንድ በአንድ ሰምታ ስታበቃም፤ አሞቷ ኮስተር አለ፡፡ ለሁሉም ገደብ አለው፡፡ ትዕግሥትም ልክ አለው፡፡ እንኳንስ በደል፤ ማርም ሲበዛ ይመራል። በደል ሲደጋገም ደግሞ ከምሬት በላይ ነው፡፡ በቃ! እንደሻውን ልትበቀለው ስመ እግዚአብሔርን ጠርታ በልቧ መሀላ
ፈጸመች፡፡
አንዱዓለም የምትወደው ታናሽ ወንድሟ፤ የተፈጸመባት ግፍ አንገብግቦት ሊበቀልላት ሄዶ ጉድ ሆኗል፡፡ እሷ ደግሞ በታናሽ ወንድሟ ላይ ለተፈጸመው ወንጀል ምላሽ መስጠት አያቅታትም፡የመጨረሻው የአባቷ ቅርስ ታያት፡፡ በክብር ተሸፍኖ በሣጥን ውስጥ በድብቅ
የተቀመጠውን፣ እሷና እናቷ ብቻ የሚያውቁትን፣ መቶ አለቃ
👍2
ድንበሩ ከጎኑ ሻጥ ያደርገው የነበረውን፤ የአሜሪካ ኩልት ሽጉጥ ከነዝናሩ...
አንዱዓለም ስለዚያ የሚያውቀው ነገር የለም፡፡ እናቷና እሷ የደበቁትም በጉርምስና ስሜት ተነሳስቶ ወንጀል ይፈጽምበታል በሚል ፍራቻ ነው።
ለረጅም ጊዜ ሥራ ፈትቶ የተኛው የአባቷ ሽጉጥ ሥራ ሊያገኝ ነው፡፡ የእንደሻው ገላ በጥይት ተበሳስቶ ወንፊት ሲሆን ታየት፡፡ እሷም ጠላቷን ጥላ በክብር ስትወድቅ ታያት...
ያለውን በሙሉ በሱ ላይ አርከፍክፋ፤ የመጨረሻዋ አንዷን እንደ ኪኒን ለመዋጥ ወሰነች፡፡ ይህንን ቃሏን እንዳለፈው ጊዜ ዳግም ላታጥፈው፣ ከዚህ በኋላ የውርደት ኑሮ ከመኖር ጠላቷን አጥፍታ
በጀግንነት ለመሞት ወስና ውሳኔዋን በፊርማዋ ካፀደቀች በኋላ፤ የሆነ
በራስ የመተማመን ስሜት ተሰማት፡፡ ነገሮች ሁሉ ቅልል ብለው ታይዋት፡፡ የምን ለሆነው ላልሆነው ማልቀስ ነው?! ኑሮ የተባለውስ የትኛው የሚያጓጓ ኑሮ ነው? :: ኑሮ እንደትንኝ ድቅቅ ብላ አንሳና ቀጭጫ ታየቻት፡፡ አሁን ነገሮች ሁሉ የመጨረሻው ደረጃ ላይ መድረሳቸውን አወቀች። ከዚህ ውሳኔዋ ፈቀቅ የሚያደርጋት አንዳችም
ሃይል አይኖርም፡፡ በቃ!!....
“አይዞህ አንዱዬ! እህትህ አለሁልህ! ደምህ እንደዚህ ሜዳ ላይ ፈስሶ አይቀርም!" ቀስ ብላ ሄዳ እዚያ ያበጠ ጉንጩ ላይ ሳም ካደረገችው በኋላ ከሆስፒታሉ ወጥታ በቀጥታ ወደ ቤቷ ሄደች...
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
አንዱዓለም ስለዚያ የሚያውቀው ነገር የለም፡፡ እናቷና እሷ የደበቁትም በጉርምስና ስሜት ተነሳስቶ ወንጀል ይፈጽምበታል በሚል ፍራቻ ነው።
ለረጅም ጊዜ ሥራ ፈትቶ የተኛው የአባቷ ሽጉጥ ሥራ ሊያገኝ ነው፡፡ የእንደሻው ገላ በጥይት ተበሳስቶ ወንፊት ሲሆን ታየት፡፡ እሷም ጠላቷን ጥላ በክብር ስትወድቅ ታያት...
ያለውን በሙሉ በሱ ላይ አርከፍክፋ፤ የመጨረሻዋ አንዷን እንደ ኪኒን ለመዋጥ ወሰነች፡፡ ይህንን ቃሏን እንዳለፈው ጊዜ ዳግም ላታጥፈው፣ ከዚህ በኋላ የውርደት ኑሮ ከመኖር ጠላቷን አጥፍታ
በጀግንነት ለመሞት ወስና ውሳኔዋን በፊርማዋ ካፀደቀች በኋላ፤ የሆነ
በራስ የመተማመን ስሜት ተሰማት፡፡ ነገሮች ሁሉ ቅልል ብለው ታይዋት፡፡ የምን ለሆነው ላልሆነው ማልቀስ ነው?! ኑሮ የተባለውስ የትኛው የሚያጓጓ ኑሮ ነው? :: ኑሮ እንደትንኝ ድቅቅ ብላ አንሳና ቀጭጫ ታየቻት፡፡ አሁን ነገሮች ሁሉ የመጨረሻው ደረጃ ላይ መድረሳቸውን አወቀች። ከዚህ ውሳኔዋ ፈቀቅ የሚያደርጋት አንዳችም
ሃይል አይኖርም፡፡ በቃ!!....
“አይዞህ አንዱዬ! እህትህ አለሁልህ! ደምህ እንደዚህ ሜዳ ላይ ፈስሶ አይቀርም!" ቀስ ብላ ሄዳ እዚያ ያበጠ ጉንጩ ላይ ሳም ካደረገችው በኋላ ከሆስፒታሉ ወጥታ በቀጥታ ወደ ቤቷ ሄደች...
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
#ክፍል_ሁለት
#ቬንዴታ
#ብቀላ
...በፈጸመባት ተደጋጋሚ ወንጀል ምክንያት ህሊናዋ ሊሸከመው
ከሚችለው በላይ በደል ያደረሰባት፤ እንደሻውን አጥፍታ፤ እራሷን ለማጥፋት የገባችውን ቃል ተግባራዊ የምታደርግበት የመጨረሻዋ ሰዓት
ከአክስቷ ጀምሮ የቅርብ የሆኑ ሰዎችን በሙሉ ተዘዋውራ ጠየቀች፡ስንብት መሆኑን አላወቁም፡፡
ውሣኔዋን ተግባራዊ የምታደርገው እንደ ነገ ሆኖ፤ ዛሬ ግን አሉኝ የምትላቸውን እናቷን፣ ወንድሟን፣ ጓደኛዋን፣ በደንብ አጫውታ መለየት አለባትና፤ የልቧን በልቧ ይዛ፤ እንደታላቅ እህቷ የምታየት፣ ደስታዋንም ሆነ ከሁሉም በላይ ችግሯን ስትጋራት የኖረች ጓደኛዋን በፍቅር ልትሰናበታት ሄደች፡፡
እንዳገኘቻት ሄዳ እላይዋ ላይ ጥምጥም ብላ አለቀሰች፡፡ አዜብም እንደሷው አቀፈቻትና ተላቀሱ፡፡
“በፍጹም እንደዚህ ያለ አደጋ ይደርስበታል ብዬ አልገመትኩም ነበር፡፡ ትሁቲና እኔ ባንቺ ምንም ዕድለኛ አልሆንኩም፡፡ የኔ ድርጊትና ምክር ሁል ጊዜ ሲጉዳሽ እንጂ ሲጠቅምሽ ባለማየቴ፤ በጣም ነው
የተሰማኝ፡፡ ከዚህ ሁሉ ለምን ትንሽ ራቅ አልልላትም የሚል ስሜት ተሰምቶኝ ነው እንጂ፣አንቺን ለማሳዘን አይደለም፡፡ ይቅርታ አድርጊልኝ” በማለት እየሳመች፤ እያባበለች፤ ይቅርታ ለመነቻት፡፡
“አዜቢና ቁጭት ተሰምቶሽ ነገርሽው እንጂ፤ እንደዚህ ጭካኔ የተሞላበት የከፋ ጉዳት ያደርስበታል ብለሽ እንዳላሰብሽ ይገባኛል። በዚህ ምንም ልትፀፀቺ አይገባም፡፡ እግዚአብሔር ገና ስፈጠር ይህንን ሁሉ መከራ እንድሸከም ፈርዶብኝ ያሸከመኝ እዳ ስለሆነ እችለዋለሁ :: አንቺ
ግን ሁሌም ስቸገር ከጉኔ ከመገኘት ሌላ ምንም ያደረግሽኝ ነገር ስለሌለ
መጥፎ ስሜት በፍጹም ሊሰማሽ አይገባም፡፡ እንኳንም ብቻ ከሞት
ተረፈ፡፡ ምንም ቅሬታ አላደረብኝም፡፡ አትጨነቂ የኔ ቆንጆ፡፡ ብላ እቅፍ አድርጋ አፅናናቻትና፤ እንደ ዱሮአቸው በፍቅር ሲጨዋወቱ አረፈዱ፡፡ለሻምበል ብሩክ ስልክ ደውላ አንዱአለም ስለደረሰበት አደጋ የነገረችው መሆኑን፤ እሱም ደንግጦ "አይዞሽ እንደሻውን ገርፈን እናውጣጣዋለን" በማለት ቃል የገባላት መሆኑን፤ እውነት አስመስላ ስትነግራት አዜብ ተደሰተች፡፡ እንደሻው የእጁን እንዲያገኝ ቸኮለች፡፡
“በጣም ቆንጆ ነው ያደረግሽው ትሁትዬ የውስጥ እግሩ ወደ ውጭ እስኪገለበጥ ድረስ እንዲያስገርፈው አድርጊ፡፡ ይሄ ግፈኛ! ለሱ ምንም ምህረት አያስፈልገውም!” ስትል በቁጭት መከረቻት፡፡ ነገ ጠዋት በፓሊስ እንደሚያስወስድላትና! የሚሰራበትን ሱቅ
ለመጠቆም፡ ዛሬ ቦታውን ማየት እንደሚያስፈልጋት ስትነግራት፤ አዜብ
ልብሷን ቶሎ ለባብሳ ተነሳች፡፡መርካቶ ሄደው የእንደሻውን ሱቅ በሩቁ አሳየቻት፡፡ ሱቁን በስንት ሰዓት እንደሚከፍት ሁሉ በቂ መረጃ አገኘች፡፡ ዋናው
የእንደሻውን ሱቅ ማየቱ ነበር፡፡
ዓላማዋ እንደሻው ውስጡ ይንጐራደዳል፡፡ ለነገው ብቀላ እንድ እርምጃ ተጠናቀቀ፡፡ እዚያ ሱቅ ውስጥ ነገ... ነገ... ጠዋት ጠላቷ ገላው፣
በጥይት ወንፊት ሆኖ የወንድሟን ደም እንዳንዠቀዠቀው፣ ደሙ ይንዠቀዠቃል....
ይህንን የነገውን ትርዒት በአእምሮዋ እያውጠነጠነች፤ ተያይዘው ወደ እነ አዜብ ቤት ተመለሱ፡፡
በመሰነባበቻቸው ሰዓት ላይ ግን የትህትና ሁኔታ ትንሽ ከወትሮው ለየት አለ፡፡ ጥብቅ አድርጋ አቀፈቻት፡፡ እያገላበጠች ሳመቻት፡፡ እንደገና ... እንደገና ... እንደገና ይህ ለአዜብ እንግዳ ነበር፡፡ ትህትና
ግን የስንብት ስለሆነ አልታወቃትም፡፡
ዐይኖቿ ፍዝዝ ብለው፤ እላይዋ ላይ ተተክለው ይቀሩ ነበር፡፡ እነዚያ ውብ ዐይኖቿ፣ ለየት ያለ መልዕክት ያስተላልፉ ነበር፡፡ ስንብት! ደህና ሁኝልኝ ውዷ ጓደኛዬ.... ዐይነት፡፡ አሁን ደግሞ ትንፋሽ
እስከሚያጥራት ድረስ አቅፋ እየተሰናበተቻት ነው፡፡ይህ የትህትና ሁኔታ
አዜብን ረበሻት፡፡
“ስላስቀየምኳት ይሆን ወይስ?...” መልስ የሌለው ጥያቄ፡፡ በመጨረሻም አገላብጣ ሳመቻትና፤ ታክሲ ውስጥ ገባች። ዞር ብላ
እጆቿን አውለበለበችላት፡፡ የምሣ ሰዓት ደርሶ ነበር፡፡ ምሣ በሁለት ሣህን
አዘጋጅታ፣ ሠራተኛዋ የካቲት አሥራ ሁለት ሆስፒታል እናቷ ጋ እንድትሄድ ስታደርግ፤ እሷ ደግሞ ወደ ወንድሟ ሄደች፡፡ ሆስፒታል ውስጥ ወንድሟን ስታጨዋውተው ዋለች፡፡ አዳሯን ደግሞ እናቷ ጋ አስባለች፡፡
የቀኑን ፕሮግራም ሙሉ ለሙሉ ለአንዱዓለም ሰጠችው፡፡ወንድሟን ለመሰናበት ስሜቷን በእንባ ለመግለጽ አልፈለገችም፡፡ ሆዷ እንዳይባባ፤ ራሷን አጠነከረች፡፡ በእርግጥም ተሳካላት፡፡ ከምንጊዜውም የበለጠ ሳቂታና ደስተኛ መስላ ታየች፡፡
እዚያ አጠገቡ ቁጭ ብላ እንዲሁ ስትደባብሰው፣ ስታሻሽው፣ ስትስመው፣ ስታሳስቀው፤ ዋለች፡፡ ሰዓቱ እየሄደ ነው፡፡ የምታዘጋጀው ደብዳቤ አለ፡፡ እናቷ ዘንድ አዳሪ ነች፡፡ ልትለየው ባትፈልግም ፤ ጣጣዋ ብዙ ነውና፤ ልትሰናበተው ተዘጋጀች፡፡
በዚያን ሰዓት ግን ቆራጥ የነበረችው ልጅ ተረታች፡፡ ሳታስበው እላዩ ላይ ድፍት እንዳለች ቀረች፡፡ ሆዷ ቡጭ ቡጭ አለ፡፡ መተንፈስ አስከሚያቅተው ደረስ እላዩ ላይ ተጣበቀች፡፡
በሽተኛ መሆኑን ዘንግታ፤ አየር አሳጠረችው፡፡ እንዱዓለም ቶሎ
ቶሎ መተንፈስ ሲጀምር፤ ደንግጣ ቀና አለችለት፡፡ በዚያን ጊዜ ግን ዕይኖቿ በእንባ ተሞልተው ነበረና፤ እንባዋ እየወረደ ፊቱን አረጠበው፡፡
“ተሽሎኛል እኮ እታለምዬ ለምን ታለቅሻለሽ?” ለመጨረሻ ጊዜ እንደምትሰናበተው ያላወቀው ወንድሟ፡፡ እየደጋገመች ሳመችው፡፡ “ደህና
ሁንልኝ አንዱዓለሜ” ከሳግ ጋር እየተናነቀች ተነሣች፡፡
“ደህና እደሪ እታለም” በአለቃቀሷ ሆዱን ባር ባር እያለው፡፡ ከዚያም ወደ ኋላ ገልመጥ አለችና ባይ ባይ " በማለት እጆቿን አወዛወዘችለት፡፡ የመጨረሻ ስንብት፡፡ ከዚያም በሚንከራተቱት ዐይኖቿ
በስስት ተሰናበተችውና፤ ፈጠን ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣች፡፡
እቤት እንደደረሰች ለሻምበል ብሩክ ደብዳቤ ትጽፍ ጀመር፡፡
“ይድረስ ለማፈቅርህ ውድ ወንድሜ ለሻምበል ብሩክ በላይ ለጤናህ እንደምን አለህልኝ፡፡ እኔ እግዚአብሔር ይመስገን በጣም ደህና ነኝ፡፡ ብሩኬ በጣም ናፍቀኸኛል፡፡ ግን ምን ያደርጋል? አልታደልኩምና ናፍቆቴን መወጣት አልችልም፡፡ይህ የመጨረሻው ቃሌ ስለሆነ አንድ ነገር ልጠይቅህ? ይህንን ደብዳቤ አንብበህ ከመጨረስህ በፊት እንዳታቋርጠው እሺ? ዛሬ የምንግርህ በሙሉ ቁም ነገር ነው እሺ? ብሩኬ መጀመሪያ ያየሁህ ዕለት የደነገጥኩብህ እኮ አባዬን ስለመሰልከኝ ነበር፡፡ አባዬ ልክ እንዳንተው እንዴት መሰለህ የሚያምረው? በተለይ የምትለብሱት
ዩኒፎርም እንዴት መሰለህ የሚያምርባችሁ። በቁመታችሁ፣ በግርማ
ሞገሳችሁ፣ በቃ ምን ልበልህ አንድ ዐይነት ናችሁ፡፡ ያኔኮ ጣቢያ መጥቼ
ቢሮህ ስገባ ደንግጬ የቀረሁት ለዚያ ነበረ፡፡ ምናልባትም የዚያን ዕለት
የተሰማኝ ስሜት በህይወቴ ውስጥ የመጀመሪያው ነበረ ብልህ ውሸታም
አድርገህ ስለቆጠርከኝ አታምነኝ ይሆናል፡፡ እንደዚያ ለወንድ ልጅ
ደንግጬ አላውቅም ነበረ፡፡ ባንተ ግን ደነገጥኩ፡፡ ከዚያም ቀስ በቀስ ወደድኩህ፡፡ ቀንም ሆነ ሌሊት አስብህ ጀመር፡፡ ስላንት ማውራት ደስ ይለኛል፡፡ እንደዚያ የሚያደርገኝ አዲስ ነገር ፍቅር መሆኑን ከኔ በፊት ያወቀችው አዜብ ነች ብልህ ይገርምህ ይሆናል፡፡ ብሩኬ ሙት አሁንም እወድሀለሁ፡፡ በእውነት እኔ እኮ ባለጌ ልጅ አልነበርኩም፡፡ የሆነውን ሁሉ
ልንገርህ? ዶክተር ባይከዳኝ ምኔም አይደለም፡፡ ምንም አላደረገኝም፡፡ ከሱ
ጋር የነበረኝ ግንኙነት እናቴን አክሞ እንዲያድንልኝ እንጂ ባንተ ላይ
ደርቤ ያፈቀረኩት ሰው ሆኖ አልነበረም አንተ ከዶክተር ባይከዳኝ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
#ክፍል_ሁለት
#ቬንዴታ
#ብቀላ
...በፈጸመባት ተደጋጋሚ ወንጀል ምክንያት ህሊናዋ ሊሸከመው
ከሚችለው በላይ በደል ያደረሰባት፤ እንደሻውን አጥፍታ፤ እራሷን ለማጥፋት የገባችውን ቃል ተግባራዊ የምታደርግበት የመጨረሻዋ ሰዓት
ከአክስቷ ጀምሮ የቅርብ የሆኑ ሰዎችን በሙሉ ተዘዋውራ ጠየቀች፡ስንብት መሆኑን አላወቁም፡፡
ውሣኔዋን ተግባራዊ የምታደርገው እንደ ነገ ሆኖ፤ ዛሬ ግን አሉኝ የምትላቸውን እናቷን፣ ወንድሟን፣ ጓደኛዋን፣ በደንብ አጫውታ መለየት አለባትና፤ የልቧን በልቧ ይዛ፤ እንደታላቅ እህቷ የምታየት፣ ደስታዋንም ሆነ ከሁሉም በላይ ችግሯን ስትጋራት የኖረች ጓደኛዋን በፍቅር ልትሰናበታት ሄደች፡፡
እንዳገኘቻት ሄዳ እላይዋ ላይ ጥምጥም ብላ አለቀሰች፡፡ አዜብም እንደሷው አቀፈቻትና ተላቀሱ፡፡
“በፍጹም እንደዚህ ያለ አደጋ ይደርስበታል ብዬ አልገመትኩም ነበር፡፡ ትሁቲና እኔ ባንቺ ምንም ዕድለኛ አልሆንኩም፡፡ የኔ ድርጊትና ምክር ሁል ጊዜ ሲጉዳሽ እንጂ ሲጠቅምሽ ባለማየቴ፤ በጣም ነው
የተሰማኝ፡፡ ከዚህ ሁሉ ለምን ትንሽ ራቅ አልልላትም የሚል ስሜት ተሰምቶኝ ነው እንጂ፣አንቺን ለማሳዘን አይደለም፡፡ ይቅርታ አድርጊልኝ” በማለት እየሳመች፤ እያባበለች፤ ይቅርታ ለመነቻት፡፡
“አዜቢና ቁጭት ተሰምቶሽ ነገርሽው እንጂ፤ እንደዚህ ጭካኔ የተሞላበት የከፋ ጉዳት ያደርስበታል ብለሽ እንዳላሰብሽ ይገባኛል። በዚህ ምንም ልትፀፀቺ አይገባም፡፡ እግዚአብሔር ገና ስፈጠር ይህንን ሁሉ መከራ እንድሸከም ፈርዶብኝ ያሸከመኝ እዳ ስለሆነ እችለዋለሁ :: አንቺ
ግን ሁሌም ስቸገር ከጉኔ ከመገኘት ሌላ ምንም ያደረግሽኝ ነገር ስለሌለ
መጥፎ ስሜት በፍጹም ሊሰማሽ አይገባም፡፡ እንኳንም ብቻ ከሞት
ተረፈ፡፡ ምንም ቅሬታ አላደረብኝም፡፡ አትጨነቂ የኔ ቆንጆ፡፡ ብላ እቅፍ አድርጋ አፅናናቻትና፤ እንደ ዱሮአቸው በፍቅር ሲጨዋወቱ አረፈዱ፡፡ለሻምበል ብሩክ ስልክ ደውላ አንዱአለም ስለደረሰበት አደጋ የነገረችው መሆኑን፤ እሱም ደንግጦ "አይዞሽ እንደሻውን ገርፈን እናውጣጣዋለን" በማለት ቃል የገባላት መሆኑን፤ እውነት አስመስላ ስትነግራት አዜብ ተደሰተች፡፡ እንደሻው የእጁን እንዲያገኝ ቸኮለች፡፡
“በጣም ቆንጆ ነው ያደረግሽው ትሁትዬ የውስጥ እግሩ ወደ ውጭ እስኪገለበጥ ድረስ እንዲያስገርፈው አድርጊ፡፡ ይሄ ግፈኛ! ለሱ ምንም ምህረት አያስፈልገውም!” ስትል በቁጭት መከረቻት፡፡ ነገ ጠዋት በፓሊስ እንደሚያስወስድላትና! የሚሰራበትን ሱቅ
ለመጠቆም፡ ዛሬ ቦታውን ማየት እንደሚያስፈልጋት ስትነግራት፤ አዜብ
ልብሷን ቶሎ ለባብሳ ተነሳች፡፡መርካቶ ሄደው የእንደሻውን ሱቅ በሩቁ አሳየቻት፡፡ ሱቁን በስንት ሰዓት እንደሚከፍት ሁሉ በቂ መረጃ አገኘች፡፡ ዋናው
የእንደሻውን ሱቅ ማየቱ ነበር፡፡
ዓላማዋ እንደሻው ውስጡ ይንጐራደዳል፡፡ ለነገው ብቀላ እንድ እርምጃ ተጠናቀቀ፡፡ እዚያ ሱቅ ውስጥ ነገ... ነገ... ጠዋት ጠላቷ ገላው፣
በጥይት ወንፊት ሆኖ የወንድሟን ደም እንዳንዠቀዠቀው፣ ደሙ ይንዠቀዠቃል....
ይህንን የነገውን ትርዒት በአእምሮዋ እያውጠነጠነች፤ ተያይዘው ወደ እነ አዜብ ቤት ተመለሱ፡፡
በመሰነባበቻቸው ሰዓት ላይ ግን የትህትና ሁኔታ ትንሽ ከወትሮው ለየት አለ፡፡ ጥብቅ አድርጋ አቀፈቻት፡፡ እያገላበጠች ሳመቻት፡፡ እንደገና ... እንደገና ... እንደገና ይህ ለአዜብ እንግዳ ነበር፡፡ ትህትና
ግን የስንብት ስለሆነ አልታወቃትም፡፡
ዐይኖቿ ፍዝዝ ብለው፤ እላይዋ ላይ ተተክለው ይቀሩ ነበር፡፡ እነዚያ ውብ ዐይኖቿ፣ ለየት ያለ መልዕክት ያስተላልፉ ነበር፡፡ ስንብት! ደህና ሁኝልኝ ውዷ ጓደኛዬ.... ዐይነት፡፡ አሁን ደግሞ ትንፋሽ
እስከሚያጥራት ድረስ አቅፋ እየተሰናበተቻት ነው፡፡ይህ የትህትና ሁኔታ
አዜብን ረበሻት፡፡
“ስላስቀየምኳት ይሆን ወይስ?...” መልስ የሌለው ጥያቄ፡፡ በመጨረሻም አገላብጣ ሳመቻትና፤ ታክሲ ውስጥ ገባች። ዞር ብላ
እጆቿን አውለበለበችላት፡፡ የምሣ ሰዓት ደርሶ ነበር፡፡ ምሣ በሁለት ሣህን
አዘጋጅታ፣ ሠራተኛዋ የካቲት አሥራ ሁለት ሆስፒታል እናቷ ጋ እንድትሄድ ስታደርግ፤ እሷ ደግሞ ወደ ወንድሟ ሄደች፡፡ ሆስፒታል ውስጥ ወንድሟን ስታጨዋውተው ዋለች፡፡ አዳሯን ደግሞ እናቷ ጋ አስባለች፡፡
የቀኑን ፕሮግራም ሙሉ ለሙሉ ለአንዱዓለም ሰጠችው፡፡ወንድሟን ለመሰናበት ስሜቷን በእንባ ለመግለጽ አልፈለገችም፡፡ ሆዷ እንዳይባባ፤ ራሷን አጠነከረች፡፡ በእርግጥም ተሳካላት፡፡ ከምንጊዜውም የበለጠ ሳቂታና ደስተኛ መስላ ታየች፡፡
እዚያ አጠገቡ ቁጭ ብላ እንዲሁ ስትደባብሰው፣ ስታሻሽው፣ ስትስመው፣ ስታሳስቀው፤ ዋለች፡፡ ሰዓቱ እየሄደ ነው፡፡ የምታዘጋጀው ደብዳቤ አለ፡፡ እናቷ ዘንድ አዳሪ ነች፡፡ ልትለየው ባትፈልግም ፤ ጣጣዋ ብዙ ነውና፤ ልትሰናበተው ተዘጋጀች፡፡
በዚያን ሰዓት ግን ቆራጥ የነበረችው ልጅ ተረታች፡፡ ሳታስበው እላዩ ላይ ድፍት እንዳለች ቀረች፡፡ ሆዷ ቡጭ ቡጭ አለ፡፡ መተንፈስ አስከሚያቅተው ደረስ እላዩ ላይ ተጣበቀች፡፡
በሽተኛ መሆኑን ዘንግታ፤ አየር አሳጠረችው፡፡ እንዱዓለም ቶሎ
ቶሎ መተንፈስ ሲጀምር፤ ደንግጣ ቀና አለችለት፡፡ በዚያን ጊዜ ግን ዕይኖቿ በእንባ ተሞልተው ነበረና፤ እንባዋ እየወረደ ፊቱን አረጠበው፡፡
“ተሽሎኛል እኮ እታለምዬ ለምን ታለቅሻለሽ?” ለመጨረሻ ጊዜ እንደምትሰናበተው ያላወቀው ወንድሟ፡፡ እየደጋገመች ሳመችው፡፡ “ደህና
ሁንልኝ አንዱዓለሜ” ከሳግ ጋር እየተናነቀች ተነሣች፡፡
“ደህና እደሪ እታለም” በአለቃቀሷ ሆዱን ባር ባር እያለው፡፡ ከዚያም ወደ ኋላ ገልመጥ አለችና ባይ ባይ " በማለት እጆቿን አወዛወዘችለት፡፡ የመጨረሻ ስንብት፡፡ ከዚያም በሚንከራተቱት ዐይኖቿ
በስስት ተሰናበተችውና፤ ፈጠን ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣች፡፡
እቤት እንደደረሰች ለሻምበል ብሩክ ደብዳቤ ትጽፍ ጀመር፡፡
“ይድረስ ለማፈቅርህ ውድ ወንድሜ ለሻምበል ብሩክ በላይ ለጤናህ እንደምን አለህልኝ፡፡ እኔ እግዚአብሔር ይመስገን በጣም ደህና ነኝ፡፡ ብሩኬ በጣም ናፍቀኸኛል፡፡ ግን ምን ያደርጋል? አልታደልኩምና ናፍቆቴን መወጣት አልችልም፡፡ይህ የመጨረሻው ቃሌ ስለሆነ አንድ ነገር ልጠይቅህ? ይህንን ደብዳቤ አንብበህ ከመጨረስህ በፊት እንዳታቋርጠው እሺ? ዛሬ የምንግርህ በሙሉ ቁም ነገር ነው እሺ? ብሩኬ መጀመሪያ ያየሁህ ዕለት የደነገጥኩብህ እኮ አባዬን ስለመሰልከኝ ነበር፡፡ አባዬ ልክ እንዳንተው እንዴት መሰለህ የሚያምረው? በተለይ የምትለብሱት
ዩኒፎርም እንዴት መሰለህ የሚያምርባችሁ። በቁመታችሁ፣ በግርማ
ሞገሳችሁ፣ በቃ ምን ልበልህ አንድ ዐይነት ናችሁ፡፡ ያኔኮ ጣቢያ መጥቼ
ቢሮህ ስገባ ደንግጬ የቀረሁት ለዚያ ነበረ፡፡ ምናልባትም የዚያን ዕለት
የተሰማኝ ስሜት በህይወቴ ውስጥ የመጀመሪያው ነበረ ብልህ ውሸታም
አድርገህ ስለቆጠርከኝ አታምነኝ ይሆናል፡፡ እንደዚያ ለወንድ ልጅ
ደንግጬ አላውቅም ነበረ፡፡ ባንተ ግን ደነገጥኩ፡፡ ከዚያም ቀስ በቀስ ወደድኩህ፡፡ ቀንም ሆነ ሌሊት አስብህ ጀመር፡፡ ስላንት ማውራት ደስ ይለኛል፡፡ እንደዚያ የሚያደርገኝ አዲስ ነገር ፍቅር መሆኑን ከኔ በፊት ያወቀችው አዜብ ነች ብልህ ይገርምህ ይሆናል፡፡ ብሩኬ ሙት አሁንም እወድሀለሁ፡፡ በእውነት እኔ እኮ ባለጌ ልጅ አልነበርኩም፡፡ የሆነውን ሁሉ
ልንገርህ? ዶክተር ባይከዳኝ ምኔም አይደለም፡፡ ምንም አላደረገኝም፡፡ ከሱ
ጋር የነበረኝ ግንኙነት እናቴን አክሞ እንዲያድንልኝ እንጂ ባንተ ላይ
ደርቤ ያፈቀረኩት ሰው ሆኖ አልነበረም አንተ ከዶክተር ባይከዳኝ
👍3
ጋር ሆኜ ባየኸኝ ወቅት ላይ እንደሻው ከአበራ ጋር ተመሳጥረው ምን እንዳደረጉኝ ዝርዝሩን አዜቢና ትነግርሃለች፡፡ እሷ ሁሉንም ነገር ታውቀዋለች፡፡ ብሩኬ እኔኮ ሸርሙጣ አይደለሁም? ዶክተር ባይከዳኝ ግን
እንደዚያ ብሎ ሰደበኝ፡፡ እማዬም በጡት ካንሰር በሽታ መታመሟንና የማትድን መሆኗን በጭካኔ ነገረኝ፡፡ የምሰቃየው እኮ እሷ እንድትድንልኝ ነበረ፡፡ ከሷ ቀጥሎ አንዱዓለሜንና አንተን ነጥዬ አላያችሁም አንተንም አጣሁህ፡፡ አንተን ያጣሁህ እንደሻው አስገድዶ ክብረ ንጽህናዬን
በመድፈር፤ በፈጸመብኝ ወንጀል ምክንያት ነው፡፡ አንዱዬ እንደሻው ምን እንዳደረገኝ ከአዜብ ሰምቶ ሄዶ ቢያነጋግረው፤ እንዳይሞት እንዳይድን አድርጎ አስደብድቦት፤ አሁን ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ገብቷል፡፡እንደሻው በዓለም ላይ አሉኝ የምላቸውን ሁሉ እንዳጣ ያላደረገው ጥረት የለም፡፡ ግፍ ሠራብኝ ብዬ ግን አልተከታተልኩም ነበረ፡፡ ብተወው
አልተውሽ አለኝ፡፡ ሴት ነች፡፡ ምን እባቷ ታደርገኛለች ብሎ ነው አይደለም? እኔ ግን እሱ እንደገመተኝ ፈሪ አይደለሁም፡፡ የወታደር ልጅ ነኝ እኮ፡፡ አባዬ የአገር ጥቃት ሊከላከል ሄዶ አይደል የቀረው? እኔ ሴቷ ልጁ ደግሞ የወንድሜንና የራሴን ጥቃት መከላከል ያቅተኛል? አያቅተኝም፡፡ ቢያንስ፤ ቢያንስ፤ እንደዚህ እንደ አሁኑ ገድሎ መሞት አያቅተኝም፡፡ ከዚህ በኋላ ያለው ህይወቴ እኮ ጨለማ ነው፡፡ እናቴ
አትድንም፡፡ የማፈቅርህ ጓደኛዬ አንተንም አጥቼሃለሁ። እንዱዓለሜ ተጉድቷል፡፡ ታዲያ ይህንን ሁሉ ስቃይ ተሸክሞ ያለ አባት ከመኖር መሞት አይሻልም? ብሩኬ ሙት በጣም ይሻላል እግዚአብሔር ለምን በዚህ ሁሉ ቅጣት ሊቀጣኝ እንደፈለገ ሳስበው አንዳንዴ ይገርመኝና፤ መኖሩንም ያጠራጥረኛል፡፡ አሁን ግን አግዚአብሔርን የምወቅስበት፣ ወይንም መኖሩን የምጠራጠርበት ጊዜ አይደለም፡፡ በደሌን ይቅር እንዲለኝ የምለምንበት ጊዜ ነው፡፡ ብሩኬ እኔን አላመንከኝም አይደል? አዜቢናን ግን ስለሁሉም ነገር ጠይቃት፡፡ እሷ ሁሉንም ነገር አንድ በአንድ ታስረዳሃለች፡፡ የነገርኩህ ሁሉ እውነት ልብወለድ ያለመሆኑን፤ ታረጋግጥልሀለች፡፡ ብሩኬ ካለኔ ተስፋ የሌላቸውን መሆኑን፤
እንዱዓለሜንና እማዬን ሆስፒታል ሄደህ ዐይናቸውን እይልኝ እሺ?
ብትችል ሆስፒታል ውስጥ ከመሞቷ በፊት ቤቷ ገብታ እንድትሞትና የመቃብሯን ሳጥን አደራ ልበልህ ?፡ የዚያን ጊዜ እሪ! ብዬ ያለቀስኩት ደግሞ ለምን እንደሆነ አዜብ ትነግርሃለች፡፡ በቃ እንዳላጣህ ነበር፡፡ነገር ከሆነ በኋላ እንዳጣህ አልፈለግሁም፡፡ ፈራሁ፡፡ የምታምነኝ ስላልመሰለኝ ፈራሁ እውነቱን
አዜብ ጋር ተመካከርንና እንደሱ እንዳደርግ ተስማማንበት፡፡ በህይወቴ
የማስታውስው የሰራሁት ትልቁ ሀጢአት ቢኖር እሱ ይመሰለኛል፡፡ ባንተ
ላይ እንደዚያ አይነት ስራ ከምስራ! እውነቱን ነግሬህ እንደ ዶክትር
አዋርደህ፤ ብታባርረኝ ይሻለኝ ነበረ፡፡ አንተን ማስቀየም በጣም ከባድ ነገር ነው እንደዚያም ሆኖ ግን አልተሳካልኝም፡፡
ከሽፈ፡፡ ነገሩ ሁሉ አሳዛኝ ሆነ፡፡ አንድ ነገር ልንገርህ ብሩኬ? ከሁሉ የሚበልጠው ክብረ ህሊና እንጂ ክብረ ንጽህና እንደሻውን በመሰለ ጨካኝ ሰውም ሊጠፋ የሚችል ስለሆነ፤ ትልቅ ግምት አትስጠው እሺ?፡፡ ዋናው ፍቅር ነው፡፡ በመጨረሻ ላይ አደራ የምልህ አንድ ነገር አለ፡፡ የሁለታችን እህል ውሃ ሊያበቃ ሰሞን፤ በህልሜ አብረን በመናፈሻ ውስጥ
ስንንሸራሽር፤ የሰጠኸኝ ጽጌረዳ እጄ ላይ ደርቃ አየሁ፡፡ እውነትም ህልሜ እውን ሆነ፡፡ ፍቅራችን ደረቀ፡፡ አሁን አደራ የምልህ በመቃብሬ ላይ እሷን የምትመስል አንድ ጽጌረዳ እንድትተክልልኝ ነው ።እሺ ብሩኬ? ነፍሴ
በሷ እንኳን ትለምልም እስቲ፡፡ ብሩኬ ልለይህ ነው፡፡ አሁን ሁሉም ነገር
አብቅቷል፡፡ በወሰድኩት እርምጃ ደግሞ ምንም ዐይነት ፀፀት እንዳይሰማህ
እሺ ?፡፡ ብሩኬ አንተ እኮ ወርቅ ሰው ነህ፡ ምንም አልበደልከኝም፡፡ እንደ ዶክተር ባይከዳኝ ሞራሌን ነክተህ አዋርደህ አላባረርከኝም፡፡ አጽናንተህ፤ አባብለህ፤ ነው የሸኘኝ :: ስለዚህ ምንም አይነት ጸጸት ሊያድርብህ አይገባም፡፡ በልጅነቴ የማውቀው አቢላዛር ምንም በማያውቀው ነገር አባቱ ለስቃይ እንደዳረገው ሁሉ፤ አንተ በማታውቀው፤ እኔም በደረሰብኝ መጥፎ አጋጣሚና ምክንያት፤ ህይወቴ ለስቃይ ተዳረገች እንጂ፤ እኔና አንተ ሳንግባባ ቀርተን የተፈጠረ ችግር ባለመኖሩ፤ በእኔ እምነት
ሁለታችንም በደለኞች አይደለንም ብሩኬ ይህ ደብዳቤ በሚደርስህ ስዓት
እርግጠኛ ነኝ ሁሉም ነገር አብቅቶ ታገኘዋለህ፡፡ መርካቶ ገበያ አዳራሽ
አካባቢ፤ ጠላቴን እንደሻውን ጥዬ ወድቄአለሁ፡፡ ለአዜቢና በ97 11 11
ደውለህ ንገራት፡፡ ብሩኬ እውድሃለሁ፡፡ ለፍቅር የመጀመሪያዬም፣ የመጨረሻዬም አንተው ብቻ እንደነበርክ በዚች በመጨረሻዋ ሰአት እንኳ ልብህ ሙሉ በሙሉ አምኖ እንዲቀበለኝ እለምንሃለሁ፡፡ ብሩኬ በቀሪው ዘመንህ መልካሙ
እንዲገጥምህ ነፍሴ ትመኝልሃለች ወንድሞችህን ተሰናበትልኝ፡፡ ደህና ሁንልኝ፡፡
እስከወዲያኛው አፍቃሪ እህትህ ትህትና ድንበሩ፡፡ ደብዳቤውን ጽፋ ካበቃች በኋላ መኝታ ክፍሏ ውስጥ ገባችና ቆለፈችው
በሩን ከዚያም ሽጉጡን ከማኀደሩ አወጣችና፤ በሚገባ ወለወለችው፡፡
ውስጡ የነበሩትን ጥይቶች አውጥታ ወደ
ጎን ካስቀመጠች በኋላ ፤ ከዝናሩ ላይ እየለቀመች አዲስ አዲስ የመሰሏትን
ስድስት ጥይቶች ለየች ፡፡ ከዚያም ሽጉጡን ባዶውን ቀጭ ቋ ! ቀጭ
እያደረገች ደጋግማ ምላጩን ሳበች፡፡
ሽጉጡን ዘቅዝቃ! ጥይቶቹ የሚገቡበትን ቀዳዳዎቹን አፀዳዳችና አሁንም ደጋግማ ሳበችው፡፡ቀጭ! ቀጭ! ቀጭ! እያለ የጥይት አቃፊው ተሽከረከረ፡፡ ከዚያም
ጥይቶቹን ሙሉ ለሙሉ አጉርሳ ስታበቃ፤ ሽጉጡን በቀኝ እጇ ይዛ፤ ፊት ለፊት ደቀነችና፤ ግራ ዓይኗን ጨፍና፤ አነጣጠረች በጠላቷ ላይ...
በመጨረሻም ቀስ ብላ መጠበቂያውን አጠበቀችና፤ በጨርቅ ከጠቀለለችው
በኋላ፤ በእጅ ቦርሣዋ ውስጥ አስቀመጠችው፡፡
አሁን ከምሽቱ አሥራ ሁለት ሰዓት ሆኗል፡፡ መጀመሪያ ለሻምበል ብሩክ የጻፈችለትን ደብዳቤ መሥሪያ ቤቱ ልታደርስ፣ ከዚያም
በኋላ እናቷጋ አድራ በጠዋት ወደ መርካቶ ለመሄድ አቀደች፡፡
ከቀኑ አሥራ ሁለት ሰዓት ተኩል ሆኗል፡፡ ሻምበል ብሩክ ከሥራ ወጥቶ ወደ ቤቱ ሄዷል፡፡ ያለመኖሩን ካረጋገጠች በኋላ፤
ተረኛውን ፖሊስ አነጋገረችው፡፡
ከክፍለ ሀገር የመጣች ዘመዱ መሆኗን አስረዳችና፤ ጠዋት ሥራ ሲገባ ፓስታውን እንዲሰጥላት ጠየቀችው፡፡
“እሺ የኔ ቆንጆ ጠዋት እንደገባ እስጥልሻለሁ” አላት፡፡
“አደራ” አለችው፡፡
“ኧረ ችግር የለም እንኳን የሻምበል ብሩክን የሌላም መልዕክት እናደርሳለን፡፡ ግድ የለሽም አይመቸኝም አልሽ እንጂ፤ ጠዋት ብትመጪ ታገኝው ነበር” አላት፡፡
“እንደገባ ይስጡልኝ፡፡ እንዳይረሱት” በማለት አደራዋን ጠበቅ አድርጋ፤ ከፓስታው ላይ “ለሻምበል ብሩክ በላይ በእጅ የሚሰጥ የአደራ ደብዳቤ” የሚል ጻፈችበት፡፡
ፖሊሱ ተቀበላትና፤ ደብዳቤውን ከኪሱ አኖረው፡፡ “ እግዜር ይስጥልኝ” በማለት ከወዲሁ ምስጋናዋን አቅርባ፤ ለመጨረሻ ጊዜ የምትሰናበታት እናቷ ዘንድ ለማደር፤ ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ሄደች፡፡
እናቷን አቅፋ ስማ፤ እህል አቅምሳት፤ አጠገቧ ሆና፤ የሆነ ያልሆነውን ስታወራላት፤ አመሸች፡፡
“አንዱዓለሜስ ምነው ብቅ አላለ?” ስትል ጠየቀቻት፡፡ ፈተና ስለደረሰበት ከጓደኞቹ ጋር ይህችን ሰሞን ጠንክሮ እያጠና መሆኑን ነገረቻት፡፡
“ይሁን ይበርታ” ብላ! እንዲቀናው ከልቧ ተመኝታ፤ ከሴት ልጇ ጋር በሰፊው ሲጫወቱ አመሹ፡፡.....
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
እንደዚያ ብሎ ሰደበኝ፡፡ እማዬም በጡት ካንሰር በሽታ መታመሟንና የማትድን መሆኗን በጭካኔ ነገረኝ፡፡ የምሰቃየው እኮ እሷ እንድትድንልኝ ነበረ፡፡ ከሷ ቀጥሎ አንዱዓለሜንና አንተን ነጥዬ አላያችሁም አንተንም አጣሁህ፡፡ አንተን ያጣሁህ እንደሻው አስገድዶ ክብረ ንጽህናዬን
በመድፈር፤ በፈጸመብኝ ወንጀል ምክንያት ነው፡፡ አንዱዬ እንደሻው ምን እንዳደረገኝ ከአዜብ ሰምቶ ሄዶ ቢያነጋግረው፤ እንዳይሞት እንዳይድን አድርጎ አስደብድቦት፤ አሁን ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ገብቷል፡፡እንደሻው በዓለም ላይ አሉኝ የምላቸውን ሁሉ እንዳጣ ያላደረገው ጥረት የለም፡፡ ግፍ ሠራብኝ ብዬ ግን አልተከታተልኩም ነበረ፡፡ ብተወው
አልተውሽ አለኝ፡፡ ሴት ነች፡፡ ምን እባቷ ታደርገኛለች ብሎ ነው አይደለም? እኔ ግን እሱ እንደገመተኝ ፈሪ አይደለሁም፡፡ የወታደር ልጅ ነኝ እኮ፡፡ አባዬ የአገር ጥቃት ሊከላከል ሄዶ አይደል የቀረው? እኔ ሴቷ ልጁ ደግሞ የወንድሜንና የራሴን ጥቃት መከላከል ያቅተኛል? አያቅተኝም፡፡ ቢያንስ፤ ቢያንስ፤ እንደዚህ እንደ አሁኑ ገድሎ መሞት አያቅተኝም፡፡ ከዚህ በኋላ ያለው ህይወቴ እኮ ጨለማ ነው፡፡ እናቴ
አትድንም፡፡ የማፈቅርህ ጓደኛዬ አንተንም አጥቼሃለሁ። እንዱዓለሜ ተጉድቷል፡፡ ታዲያ ይህንን ሁሉ ስቃይ ተሸክሞ ያለ አባት ከመኖር መሞት አይሻልም? ብሩኬ ሙት በጣም ይሻላል እግዚአብሔር ለምን በዚህ ሁሉ ቅጣት ሊቀጣኝ እንደፈለገ ሳስበው አንዳንዴ ይገርመኝና፤ መኖሩንም ያጠራጥረኛል፡፡ አሁን ግን አግዚአብሔርን የምወቅስበት፣ ወይንም መኖሩን የምጠራጠርበት ጊዜ አይደለም፡፡ በደሌን ይቅር እንዲለኝ የምለምንበት ጊዜ ነው፡፡ ብሩኬ እኔን አላመንከኝም አይደል? አዜቢናን ግን ስለሁሉም ነገር ጠይቃት፡፡ እሷ ሁሉንም ነገር አንድ በአንድ ታስረዳሃለች፡፡ የነገርኩህ ሁሉ እውነት ልብወለድ ያለመሆኑን፤ ታረጋግጥልሀለች፡፡ ብሩኬ ካለኔ ተስፋ የሌላቸውን መሆኑን፤
እንዱዓለሜንና እማዬን ሆስፒታል ሄደህ ዐይናቸውን እይልኝ እሺ?
ብትችል ሆስፒታል ውስጥ ከመሞቷ በፊት ቤቷ ገብታ እንድትሞትና የመቃብሯን ሳጥን አደራ ልበልህ ?፡ የዚያን ጊዜ እሪ! ብዬ ያለቀስኩት ደግሞ ለምን እንደሆነ አዜብ ትነግርሃለች፡፡ በቃ እንዳላጣህ ነበር፡፡ነገር ከሆነ በኋላ እንዳጣህ አልፈለግሁም፡፡ ፈራሁ፡፡ የምታምነኝ ስላልመሰለኝ ፈራሁ እውነቱን
አዜብ ጋር ተመካከርንና እንደሱ እንዳደርግ ተስማማንበት፡፡ በህይወቴ
የማስታውስው የሰራሁት ትልቁ ሀጢአት ቢኖር እሱ ይመሰለኛል፡፡ ባንተ
ላይ እንደዚያ አይነት ስራ ከምስራ! እውነቱን ነግሬህ እንደ ዶክትር
አዋርደህ፤ ብታባርረኝ ይሻለኝ ነበረ፡፡ አንተን ማስቀየም በጣም ከባድ ነገር ነው እንደዚያም ሆኖ ግን አልተሳካልኝም፡፡
ከሽፈ፡፡ ነገሩ ሁሉ አሳዛኝ ሆነ፡፡ አንድ ነገር ልንገርህ ብሩኬ? ከሁሉ የሚበልጠው ክብረ ህሊና እንጂ ክብረ ንጽህና እንደሻውን በመሰለ ጨካኝ ሰውም ሊጠፋ የሚችል ስለሆነ፤ ትልቅ ግምት አትስጠው እሺ?፡፡ ዋናው ፍቅር ነው፡፡ በመጨረሻ ላይ አደራ የምልህ አንድ ነገር አለ፡፡ የሁለታችን እህል ውሃ ሊያበቃ ሰሞን፤ በህልሜ አብረን በመናፈሻ ውስጥ
ስንንሸራሽር፤ የሰጠኸኝ ጽጌረዳ እጄ ላይ ደርቃ አየሁ፡፡ እውነትም ህልሜ እውን ሆነ፡፡ ፍቅራችን ደረቀ፡፡ አሁን አደራ የምልህ በመቃብሬ ላይ እሷን የምትመስል አንድ ጽጌረዳ እንድትተክልልኝ ነው ።እሺ ብሩኬ? ነፍሴ
በሷ እንኳን ትለምልም እስቲ፡፡ ብሩኬ ልለይህ ነው፡፡ አሁን ሁሉም ነገር
አብቅቷል፡፡ በወሰድኩት እርምጃ ደግሞ ምንም ዐይነት ፀፀት እንዳይሰማህ
እሺ ?፡፡ ብሩኬ አንተ እኮ ወርቅ ሰው ነህ፡ ምንም አልበደልከኝም፡፡ እንደ ዶክተር ባይከዳኝ ሞራሌን ነክተህ አዋርደህ አላባረርከኝም፡፡ አጽናንተህ፤ አባብለህ፤ ነው የሸኘኝ :: ስለዚህ ምንም አይነት ጸጸት ሊያድርብህ አይገባም፡፡ በልጅነቴ የማውቀው አቢላዛር ምንም በማያውቀው ነገር አባቱ ለስቃይ እንደዳረገው ሁሉ፤ አንተ በማታውቀው፤ እኔም በደረሰብኝ መጥፎ አጋጣሚና ምክንያት፤ ህይወቴ ለስቃይ ተዳረገች እንጂ፤ እኔና አንተ ሳንግባባ ቀርተን የተፈጠረ ችግር ባለመኖሩ፤ በእኔ እምነት
ሁለታችንም በደለኞች አይደለንም ብሩኬ ይህ ደብዳቤ በሚደርስህ ስዓት
እርግጠኛ ነኝ ሁሉም ነገር አብቅቶ ታገኘዋለህ፡፡ መርካቶ ገበያ አዳራሽ
አካባቢ፤ ጠላቴን እንደሻውን ጥዬ ወድቄአለሁ፡፡ ለአዜቢና በ97 11 11
ደውለህ ንገራት፡፡ ብሩኬ እውድሃለሁ፡፡ ለፍቅር የመጀመሪያዬም፣ የመጨረሻዬም አንተው ብቻ እንደነበርክ በዚች በመጨረሻዋ ሰአት እንኳ ልብህ ሙሉ በሙሉ አምኖ እንዲቀበለኝ እለምንሃለሁ፡፡ ብሩኬ በቀሪው ዘመንህ መልካሙ
እንዲገጥምህ ነፍሴ ትመኝልሃለች ወንድሞችህን ተሰናበትልኝ፡፡ ደህና ሁንልኝ፡፡
እስከወዲያኛው አፍቃሪ እህትህ ትህትና ድንበሩ፡፡ ደብዳቤውን ጽፋ ካበቃች በኋላ መኝታ ክፍሏ ውስጥ ገባችና ቆለፈችው
በሩን ከዚያም ሽጉጡን ከማኀደሩ አወጣችና፤ በሚገባ ወለወለችው፡፡
ውስጡ የነበሩትን ጥይቶች አውጥታ ወደ
ጎን ካስቀመጠች በኋላ ፤ ከዝናሩ ላይ እየለቀመች አዲስ አዲስ የመሰሏትን
ስድስት ጥይቶች ለየች ፡፡ ከዚያም ሽጉጡን ባዶውን ቀጭ ቋ ! ቀጭ
እያደረገች ደጋግማ ምላጩን ሳበች፡፡
ሽጉጡን ዘቅዝቃ! ጥይቶቹ የሚገቡበትን ቀዳዳዎቹን አፀዳዳችና አሁንም ደጋግማ ሳበችው፡፡ቀጭ! ቀጭ! ቀጭ! እያለ የጥይት አቃፊው ተሽከረከረ፡፡ ከዚያም
ጥይቶቹን ሙሉ ለሙሉ አጉርሳ ስታበቃ፤ ሽጉጡን በቀኝ እጇ ይዛ፤ ፊት ለፊት ደቀነችና፤ ግራ ዓይኗን ጨፍና፤ አነጣጠረች በጠላቷ ላይ...
በመጨረሻም ቀስ ብላ መጠበቂያውን አጠበቀችና፤ በጨርቅ ከጠቀለለችው
በኋላ፤ በእጅ ቦርሣዋ ውስጥ አስቀመጠችው፡፡
አሁን ከምሽቱ አሥራ ሁለት ሰዓት ሆኗል፡፡ መጀመሪያ ለሻምበል ብሩክ የጻፈችለትን ደብዳቤ መሥሪያ ቤቱ ልታደርስ፣ ከዚያም
በኋላ እናቷጋ አድራ በጠዋት ወደ መርካቶ ለመሄድ አቀደች፡፡
ከቀኑ አሥራ ሁለት ሰዓት ተኩል ሆኗል፡፡ ሻምበል ብሩክ ከሥራ ወጥቶ ወደ ቤቱ ሄዷል፡፡ ያለመኖሩን ካረጋገጠች በኋላ፤
ተረኛውን ፖሊስ አነጋገረችው፡፡
ከክፍለ ሀገር የመጣች ዘመዱ መሆኗን አስረዳችና፤ ጠዋት ሥራ ሲገባ ፓስታውን እንዲሰጥላት ጠየቀችው፡፡
“እሺ የኔ ቆንጆ ጠዋት እንደገባ እስጥልሻለሁ” አላት፡፡
“አደራ” አለችው፡፡
“ኧረ ችግር የለም እንኳን የሻምበል ብሩክን የሌላም መልዕክት እናደርሳለን፡፡ ግድ የለሽም አይመቸኝም አልሽ እንጂ፤ ጠዋት ብትመጪ ታገኝው ነበር” አላት፡፡
“እንደገባ ይስጡልኝ፡፡ እንዳይረሱት” በማለት አደራዋን ጠበቅ አድርጋ፤ ከፓስታው ላይ “ለሻምበል ብሩክ በላይ በእጅ የሚሰጥ የአደራ ደብዳቤ” የሚል ጻፈችበት፡፡
ፖሊሱ ተቀበላትና፤ ደብዳቤውን ከኪሱ አኖረው፡፡ “ እግዜር ይስጥልኝ” በማለት ከወዲሁ ምስጋናዋን አቅርባ፤ ለመጨረሻ ጊዜ የምትሰናበታት እናቷ ዘንድ ለማደር፤ ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ሄደች፡፡
እናቷን አቅፋ ስማ፤ እህል አቅምሳት፤ አጠገቧ ሆና፤ የሆነ ያልሆነውን ስታወራላት፤ አመሸች፡፡
“አንዱዓለሜስ ምነው ብቅ አላለ?” ስትል ጠየቀቻት፡፡ ፈተና ስለደረሰበት ከጓደኞቹ ጋር ይህችን ሰሞን ጠንክሮ እያጠና መሆኑን ነገረቻት፡፡
“ይሁን ይበርታ” ብላ! እንዲቀናው ከልቧ ተመኝታ፤ ከሴት ልጇ ጋር በሰፊው ሲጫወቱ አመሹ፡፡.....
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍3
#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
ከገና ማዕበል ያመለጠው ተማሪ፥ የዩኒቨርስቲ ውስጥ ዕድሜው መራዘሙን ካረጋገጠ በኋላ መረጋጋት ይታይበታል ። የሁለተኛው ሴሚስተር ትምህርት ቢጀመርም ገና ሞቅ ሞቅ ባለማለቱ አንገቱን መልሶ ቀለም ላይ የደፋ ተማሪ
እምብዛ!” ነው ። ሆኖም ፋታ ፈጥሮአቸው የነበሩት ቀልድ ፥ትችት።ውንጀላና ተረብ ተግ ብለዋል ።
ትዕግሥት ማጥናት አልጀመረችም ። የወረቀት ዘር ማየት ያስጠላት ትመስላለች ትምህርት ክፍሉ ውስጥ እንኳ ከመምህራኑ ገለጻ ሙሉ በሙሉ ማስታወሻ መውሰዷን ትጠራጠራለች ። ምክንያቱ አንዳንዴ ሐሳቧ እያመለጣት
ወደ ወጭ መብረር ጀምሯል ፤ በግልጽ ያልተከተላት ስሜት ሲፈታተናት ይሰማታል ከውስጧ አንዳች ነገር የጎደለ ይመስላታል። ምናልባት በቢልልኝ አገላለጽ ለፍቅር የተዘጋጀው ሥፍራ ሳይሆን አይቀርም የሚረብሻት ።
እቤል ሕመሙን አጋብቶባት እንደ ሄደ ለመገመት ብዙ ጊዜ አልወሰደባትም ። መኝታ ክፍሏ መግባት መውጣትም አስጠልቷታል ። ጸባይዋ ቢንቋሸሽም ፡ በመጠኑ ለምዳት የነበረችው ጓደኛዋ ማርታ ነበረች ። እሷ ከተባረረች ወዲህ በደንብ ቀርባ የምትጫወተውን የሴት ጓደኛ አላገኘችም ። ከቤተልሔም ጋር ዐልፎ ህልፎ ይገናኛሉ ። ሆኖም በግቢው ውስጥ የቤተልሔም ስም እየቆሸሽ ስለ መጣ ትዕግሥት አብራ እንዳትታማ በመፍራት ቀስ በቀስ እየራቀቻት
ነበር ። አቤል ግቢውን ለቅቆ ከወጣ ወዲህ ለዐይኗ ማሳረፊያ ያገኘችው ሰው እስክንድር ነው ፡ ሳታየዉ ወይም
አግኝታው የተለመደውን “ ታዲያስ ፥ ታዲያስ ” ሰላምታ ሳትለዋወጥ ውላ
አታውቅም ።
እስክንድርም ቢሆን፥የትዕግሥትን መግቢያና መውጪያ ሰዓት ጠብቆ ነው የሚገኛት ፥ ከመኝታ ክፍሉ ጠዋት
ሲወጣ ስለ አቤል ሁኔታ ፍርጥርጥ አርጎ አጫውቷት መፍትሔውን እንዲወያዩበት ሊለምናት ያስብና ፡ በሚያገኛት ጊዜ ልቡ ይከዳዋል ። በዮናታን ፊት የፎከረውንና እሷን ሲያገኛት ምላሱ መተሳስሩን ሲያመዛዝን ራሱን ታዘበው ።
“ አቤልስ ቢደነግጥላትም ቢፈራትም ወዷት ነው ፤እኔ ደግሞ ያሰብኩትን ልነግራት መፍራቴ ለምንድን ነው ? ” እያለ
ከራሱ ጋር መሟገቱ አልቀረም ። ግን ለእስክንድር አልታወቀውም እንጂ፥ ስለ አቤል ጠልቆ ሳያነሳባት ከትዕግሥት ጋር
ግንኙነቱን ማጠናከሩ ለዓላማው ጥሩ መንገድ አመቻችቶለት ነበር ። በአንዴ ነጥቡ ላይ ደርሶ ዱብ ዕዳ ከማውረድ ፥ ቀስ በቀስ አለማምዶ ከነጥቡ ላይ መድረሱን መልሱ የእሽታ እንዲሆን ይበልጥ ይረዳል ።
ትዕግሥትን ከአቤል ጋር ለማገናኘት አማራጭ መንገዶችን ዮናታንና ቢልልኝ ተነጋግረው ነበር ። ትዕግሥትን ድንገት ወስዶ አቤል ፊት ማቅረቡን ቢልልኝ አልደገፉትም ምናልባትም ካለፈው ልምዳቸው በመነሣት ሊሆን ይችላል።
አንዴ እንዲሁ ተመሳሳይ ችግር የገጠመው ተማሪ የሚፈልጋትን ልጅ አቅርበው እናስተዋውቅህ ሲሉት፡ ካልገደልኳት ብሎ የተጋበዘው ነገር ምንጊዜም አይረሳቸውም ። እና አሁን ያቀረቡት ሐሳብ በመጀመሪያ አቤል ስለ ትዕግሥት ቀና አመለካከት እንዲኖረው መኮትኮትና አጠገቡ ከመድረሷ በፊት በስልክ እንድታነጋግረው ወይም ደብዳቤ እንድትጽፍለት ማድረግ ነበር ። ደብዳቤ መጻፍዋ የተሻለ መንገድ ሆኖ ተመረጠ ። ይህን ለማስፈጸም በሙሉ ልብ ኃላፊነቱን
የወሰደው እስክንድር ነበር ። ታዲያ አሁን ተግባሩ ላይ ሲዲርስ የምን ወገቤን ያዙኝ ነው ?
ሲያምጥ ከርሞ፡አንድ ቀን እንደ ምንም ደፍሮ ሔደ ። ከመኝታ ክፍሏ አስጠራትና ፡ “ ለጥብቅ ጉዳይ እፈልግሻለሁ ” አላት ። በቆይታ የሚያወሩበት ቦታም ችግር ነበር
እነትዕግሥት ቀድሞ ያጠኑበት የነበረው ከዋናው ቤተ መጹሕፍት ጀርባ ያለው ዋርካ አካባቢ ታየው ። ግን ሁለታችንን
ብቻ እዚያ ዋርካ ሥር ሲያዩን ተማሪዎች ምን ይሉናል ? የሚል ሥጋት እደረበት በመጨረሻም ካወጣ ካወረደ በኋላ ሌላ ቦታ በማጣቱ “ ያሉትን ይበሉ ወደ
ዋርካው ሥር ይዟት ሔደ
እንዴት እንደሚጀምርላት ግራ ገብቶት ትንሽ ተጨነቀ። ግን ዝም ማለትም አልቻለም ። ዐይኖችዋ ውስጥ የጥያቄ
ምልክቶች ተደርድረው ያየ መሰለው ።
“ ሁለታችንም ሳንጠላው የምንሸሸው አርዕስት ነው አላት በድንገት ።
“ ምን ? ” አለችው ፥ ነገሩ ቢገባትም ከእሱው ይምጣ በሚል ስሜት ።
የእቤልን ነገር ሁለቱ በተገናኙ ቁጥር ዳር ዳር ሳይሉ ስለማይለያዩ አሁን ስለእሱ ሊያወራት መሆኑን ትዕግሥት አላጣቸውም ። ስሜቷን ደብቃ ነው እንጂ ወሬውን ለመስ ማት ቸኩላለች
ስለ አቤል በደንብ ላጫውትሽ ብዬ ነው ?” አላት ።
ፈቃደኛነቷን በአፏ ሳይሆን በዐይኖቿ ነው የግለጸችለት ።
አጫወታት ነው ረበሻት የሚባለው ? የለም ! ማጫወት ላይ ላዩን ሲሆን ነው ። ከሥር ከመሠረቱ ጀምሮ ልብን እያናጉ
መንፈስን እያወራጩ ፥ ቁስልን እየቀሰቀሱ ስሜትን እያንገላቱ የሚናገሩት ነገር፡ “ መረበሽ ” የሚለውን ቃል ቢይዝ ይሻላል ። እስክንድር እንደዚያ ነው ያደረገው ። ሳያስበው የእሱም ስሜት አርዕስተ ነገሩ ውስጥ ሰምጦ እየተንገላታ ስለ አቤል የሚያውቀውን ሁሉ ነገራት። እሷን ካየበት
ዕለት ጀምሮ በግሉ የተቀበለውን ሥቃይ አሁን የት እና በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ዘረዘረላት እያወራላት ገጽታዋን ገመገመ ከንፈሯ በቅጽበት ሲከስል ታየው ። ፊቷ በአንዴ ጠወለገ ። አዲስ ነገር ተናግሮ
አልረበሻትም ። አብዛኛው የምታውቀው ነገር ነው ። አብዛኛው ከአቤል ጋር አንድ ሴሚስተር ሙሉ በዐይናቸው የተለዋወጡት የጥናት ፥ የቁጣ ፥ የሥቃይና የእልህ ድምፅ አልባ
ግንኙነት ነው።
“ ታዲያ ጥፋተኛው ማነው ? ” አለችው ንግግሩን መጨረሱን ካረጋገጠች በኋላ
ዐይኖችዋ ያቀረሩትን ዕንባ ሲያይ ስሜትዋ ተጋባበት።ግን እሱ የማልቀስ ችግር አለበት ፤ዕንባው ቶሎ አይመጣለትም ።
ለፍርድ አስቸጋሪ ነው ። ሁለታችሁም ጥፋተኛች አይደላችሁም ። እየተፈላለጉ መራራቅን ፡ “ የፍቅር እንቆቅልሽ ” ብንለው ይሻላል ” አላት ።ዝም አለችው ። እሱም ዝም ብሎ ተመልከታት ። የአቤልን ስሜት ያደነዘዘውን የመልኳን ውበት ማጥናት ፈለገ ።ግን ከዳመነ ፊቷ ላይ ውበት ለማጥናት መሞከሩ አስቸጋሪ
ሆነበት ።
በረዥሙ ተነፈሰች የጭንቅ አተነፋፈስ ። የታባቱ !በሥቃይ የታመቀው አየር ወጣ ።
“ አሁን አንገብጋቢው “ ጥያቄ ጥፋተኛው ማነው?”ሳይሆን ፥ “ መፍትሔው ምንድነው ?” ይመስለኛል” አላት እስክንድር ።
“ ምን መፍትሔ አለው ? ” አለችው ፡ ተስፋ በቆረጠ ድምፅ።
“ አለው እንጂ ።አቤል ይወድሻል ፥ ይፈልግሻል ማወቅ የሚፈልገው ያንቺ ምላሽ ምን እንደሆን ነው ። ካንቺ
መረዳት እንደ ቻልኩት ደግሞ አንቺም ትፈልጊዋለሽ ፤ትወጂዋለሽ ። ይህን ስሜትሽን በደብዳቤ ብትገልጪለት
ችግሩ ይቃለላል ። ”
ደብዳቤ ”አለችው ; ሳይተዋወቁ የምትጽፍለት ደብዳቤ ምን እንደሚሆን ግር ብሏት ።
"አዎ ደብዳቤ !"
"ምን ብዬ ?"
“ በቃ ለእሱ ያለሽን ስሜት ነዋ ! ”
አሰበች ፤ደብዳቤ ። አዎ ጥሩ መንገድ ነው ስትጽፍ አጠገቧ የምታፍረው ወይም የምትፈራው አቤል አይኖርም ወረቀቱ ሳይ የምታሰፍራቸው ቃላት ፈንቅለዋት ማልቀስ ቢዳዳትም ማልቀስ ትችላለች ። ታዛቢ አይኖርባትም ። የምትጽፈው ነገር ከጭንቅላቷ ውስጥ እየፈለቀ ኣሁን አሁን
አሰኛት ።
“ ካልሆነም ረቂቁን እኔ ልጻፍልሽ ” አላት እስክንድር፡ ዝም ስትልበት ጊዜ የቸገራት መስሎት ።
ግድ የለም ፤ እኔው እሞክራለሁ ” አለችው ፥ በሐሳቧ የምትጽፍበትን ቦታ እየመረጠች ምቹ ቦታ የለም ።
የመኝታ ክፍል ጓደኞቿ ከተኙ በኋላ፥ ሌሊት ተነሥታ የመጻፍ ሐሳብ መጣላት ።
“ ጥሩ እንግዲህ ፥ ጸፊና ሰጪኝ ። እኔ አደርስልሻ
፡
፡
#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
ከገና ማዕበል ያመለጠው ተማሪ፥ የዩኒቨርስቲ ውስጥ ዕድሜው መራዘሙን ካረጋገጠ በኋላ መረጋጋት ይታይበታል ። የሁለተኛው ሴሚስተር ትምህርት ቢጀመርም ገና ሞቅ ሞቅ ባለማለቱ አንገቱን መልሶ ቀለም ላይ የደፋ ተማሪ
እምብዛ!” ነው ። ሆኖም ፋታ ፈጥሮአቸው የነበሩት ቀልድ ፥ትችት።ውንጀላና ተረብ ተግ ብለዋል ።
ትዕግሥት ማጥናት አልጀመረችም ። የወረቀት ዘር ማየት ያስጠላት ትመስላለች ትምህርት ክፍሉ ውስጥ እንኳ ከመምህራኑ ገለጻ ሙሉ በሙሉ ማስታወሻ መውሰዷን ትጠራጠራለች ። ምክንያቱ አንዳንዴ ሐሳቧ እያመለጣት
ወደ ወጭ መብረር ጀምሯል ፤ በግልጽ ያልተከተላት ስሜት ሲፈታተናት ይሰማታል ከውስጧ አንዳች ነገር የጎደለ ይመስላታል። ምናልባት በቢልልኝ አገላለጽ ለፍቅር የተዘጋጀው ሥፍራ ሳይሆን አይቀርም የሚረብሻት ።
እቤል ሕመሙን አጋብቶባት እንደ ሄደ ለመገመት ብዙ ጊዜ አልወሰደባትም ። መኝታ ክፍሏ መግባት መውጣትም አስጠልቷታል ። ጸባይዋ ቢንቋሸሽም ፡ በመጠኑ ለምዳት የነበረችው ጓደኛዋ ማርታ ነበረች ። እሷ ከተባረረች ወዲህ በደንብ ቀርባ የምትጫወተውን የሴት ጓደኛ አላገኘችም ። ከቤተልሔም ጋር ዐልፎ ህልፎ ይገናኛሉ ። ሆኖም በግቢው ውስጥ የቤተልሔም ስም እየቆሸሽ ስለ መጣ ትዕግሥት አብራ እንዳትታማ በመፍራት ቀስ በቀስ እየራቀቻት
ነበር ። አቤል ግቢውን ለቅቆ ከወጣ ወዲህ ለዐይኗ ማሳረፊያ ያገኘችው ሰው እስክንድር ነው ፡ ሳታየዉ ወይም
አግኝታው የተለመደውን “ ታዲያስ ፥ ታዲያስ ” ሰላምታ ሳትለዋወጥ ውላ
አታውቅም ።
እስክንድርም ቢሆን፥የትዕግሥትን መግቢያና መውጪያ ሰዓት ጠብቆ ነው የሚገኛት ፥ ከመኝታ ክፍሉ ጠዋት
ሲወጣ ስለ አቤል ሁኔታ ፍርጥርጥ አርጎ አጫውቷት መፍትሔውን እንዲወያዩበት ሊለምናት ያስብና ፡ በሚያገኛት ጊዜ ልቡ ይከዳዋል ። በዮናታን ፊት የፎከረውንና እሷን ሲያገኛት ምላሱ መተሳስሩን ሲያመዛዝን ራሱን ታዘበው ።
“ አቤልስ ቢደነግጥላትም ቢፈራትም ወዷት ነው ፤እኔ ደግሞ ያሰብኩትን ልነግራት መፍራቴ ለምንድን ነው ? ” እያለ
ከራሱ ጋር መሟገቱ አልቀረም ። ግን ለእስክንድር አልታወቀውም እንጂ፥ ስለ አቤል ጠልቆ ሳያነሳባት ከትዕግሥት ጋር
ግንኙነቱን ማጠናከሩ ለዓላማው ጥሩ መንገድ አመቻችቶለት ነበር ። በአንዴ ነጥቡ ላይ ደርሶ ዱብ ዕዳ ከማውረድ ፥ ቀስ በቀስ አለማምዶ ከነጥቡ ላይ መድረሱን መልሱ የእሽታ እንዲሆን ይበልጥ ይረዳል ።
ትዕግሥትን ከአቤል ጋር ለማገናኘት አማራጭ መንገዶችን ዮናታንና ቢልልኝ ተነጋግረው ነበር ። ትዕግሥትን ድንገት ወስዶ አቤል ፊት ማቅረቡን ቢልልኝ አልደገፉትም ምናልባትም ካለፈው ልምዳቸው በመነሣት ሊሆን ይችላል።
አንዴ እንዲሁ ተመሳሳይ ችግር የገጠመው ተማሪ የሚፈልጋትን ልጅ አቅርበው እናስተዋውቅህ ሲሉት፡ ካልገደልኳት ብሎ የተጋበዘው ነገር ምንጊዜም አይረሳቸውም ። እና አሁን ያቀረቡት ሐሳብ በመጀመሪያ አቤል ስለ ትዕግሥት ቀና አመለካከት እንዲኖረው መኮትኮትና አጠገቡ ከመድረሷ በፊት በስልክ እንድታነጋግረው ወይም ደብዳቤ እንድትጽፍለት ማድረግ ነበር ። ደብዳቤ መጻፍዋ የተሻለ መንገድ ሆኖ ተመረጠ ። ይህን ለማስፈጸም በሙሉ ልብ ኃላፊነቱን
የወሰደው እስክንድር ነበር ። ታዲያ አሁን ተግባሩ ላይ ሲዲርስ የምን ወገቤን ያዙኝ ነው ?
ሲያምጥ ከርሞ፡አንድ ቀን እንደ ምንም ደፍሮ ሔደ ። ከመኝታ ክፍሏ አስጠራትና ፡ “ ለጥብቅ ጉዳይ እፈልግሻለሁ ” አላት ። በቆይታ የሚያወሩበት ቦታም ችግር ነበር
እነትዕግሥት ቀድሞ ያጠኑበት የነበረው ከዋናው ቤተ መጹሕፍት ጀርባ ያለው ዋርካ አካባቢ ታየው ። ግን ሁለታችንን
ብቻ እዚያ ዋርካ ሥር ሲያዩን ተማሪዎች ምን ይሉናል ? የሚል ሥጋት እደረበት በመጨረሻም ካወጣ ካወረደ በኋላ ሌላ ቦታ በማጣቱ “ ያሉትን ይበሉ ወደ
ዋርካው ሥር ይዟት ሔደ
እንዴት እንደሚጀምርላት ግራ ገብቶት ትንሽ ተጨነቀ። ግን ዝም ማለትም አልቻለም ። ዐይኖችዋ ውስጥ የጥያቄ
ምልክቶች ተደርድረው ያየ መሰለው ።
“ ሁለታችንም ሳንጠላው የምንሸሸው አርዕስት ነው አላት በድንገት ።
“ ምን ? ” አለችው ፥ ነገሩ ቢገባትም ከእሱው ይምጣ በሚል ስሜት ።
የእቤልን ነገር ሁለቱ በተገናኙ ቁጥር ዳር ዳር ሳይሉ ስለማይለያዩ አሁን ስለእሱ ሊያወራት መሆኑን ትዕግሥት አላጣቸውም ። ስሜቷን ደብቃ ነው እንጂ ወሬውን ለመስ ማት ቸኩላለች
ስለ አቤል በደንብ ላጫውትሽ ብዬ ነው ?” አላት ።
ፈቃደኛነቷን በአፏ ሳይሆን በዐይኖቿ ነው የግለጸችለት ።
አጫወታት ነው ረበሻት የሚባለው ? የለም ! ማጫወት ላይ ላዩን ሲሆን ነው ። ከሥር ከመሠረቱ ጀምሮ ልብን እያናጉ
መንፈስን እያወራጩ ፥ ቁስልን እየቀሰቀሱ ስሜትን እያንገላቱ የሚናገሩት ነገር፡ “ መረበሽ ” የሚለውን ቃል ቢይዝ ይሻላል ። እስክንድር እንደዚያ ነው ያደረገው ። ሳያስበው የእሱም ስሜት አርዕስተ ነገሩ ውስጥ ሰምጦ እየተንገላታ ስለ አቤል የሚያውቀውን ሁሉ ነገራት። እሷን ካየበት
ዕለት ጀምሮ በግሉ የተቀበለውን ሥቃይ አሁን የት እና በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ዘረዘረላት እያወራላት ገጽታዋን ገመገመ ከንፈሯ በቅጽበት ሲከስል ታየው ። ፊቷ በአንዴ ጠወለገ ። አዲስ ነገር ተናግሮ
አልረበሻትም ። አብዛኛው የምታውቀው ነገር ነው ። አብዛኛው ከአቤል ጋር አንድ ሴሚስተር ሙሉ በዐይናቸው የተለዋወጡት የጥናት ፥ የቁጣ ፥ የሥቃይና የእልህ ድምፅ አልባ
ግንኙነት ነው።
“ ታዲያ ጥፋተኛው ማነው ? ” አለችው ንግግሩን መጨረሱን ካረጋገጠች በኋላ
ዐይኖችዋ ያቀረሩትን ዕንባ ሲያይ ስሜትዋ ተጋባበት።ግን እሱ የማልቀስ ችግር አለበት ፤ዕንባው ቶሎ አይመጣለትም ።
ለፍርድ አስቸጋሪ ነው ። ሁለታችሁም ጥፋተኛች አይደላችሁም ። እየተፈላለጉ መራራቅን ፡ “ የፍቅር እንቆቅልሽ ” ብንለው ይሻላል ” አላት ።ዝም አለችው ። እሱም ዝም ብሎ ተመልከታት ። የአቤልን ስሜት ያደነዘዘውን የመልኳን ውበት ማጥናት ፈለገ ።ግን ከዳመነ ፊቷ ላይ ውበት ለማጥናት መሞከሩ አስቸጋሪ
ሆነበት ።
በረዥሙ ተነፈሰች የጭንቅ አተነፋፈስ ። የታባቱ !በሥቃይ የታመቀው አየር ወጣ ።
“ አሁን አንገብጋቢው “ ጥያቄ ጥፋተኛው ማነው?”ሳይሆን ፥ “ መፍትሔው ምንድነው ?” ይመስለኛል” አላት እስክንድር ።
“ ምን መፍትሔ አለው ? ” አለችው ፡ ተስፋ በቆረጠ ድምፅ።
“ አለው እንጂ ።አቤል ይወድሻል ፥ ይፈልግሻል ማወቅ የሚፈልገው ያንቺ ምላሽ ምን እንደሆን ነው ። ካንቺ
መረዳት እንደ ቻልኩት ደግሞ አንቺም ትፈልጊዋለሽ ፤ትወጂዋለሽ ። ይህን ስሜትሽን በደብዳቤ ብትገልጪለት
ችግሩ ይቃለላል ። ”
ደብዳቤ ”አለችው ; ሳይተዋወቁ የምትጽፍለት ደብዳቤ ምን እንደሚሆን ግር ብሏት ።
"አዎ ደብዳቤ !"
"ምን ብዬ ?"
“ በቃ ለእሱ ያለሽን ስሜት ነዋ ! ”
አሰበች ፤ደብዳቤ ። አዎ ጥሩ መንገድ ነው ስትጽፍ አጠገቧ የምታፍረው ወይም የምትፈራው አቤል አይኖርም ወረቀቱ ሳይ የምታሰፍራቸው ቃላት ፈንቅለዋት ማልቀስ ቢዳዳትም ማልቀስ ትችላለች ። ታዛቢ አይኖርባትም ። የምትጽፈው ነገር ከጭንቅላቷ ውስጥ እየፈለቀ ኣሁን አሁን
አሰኛት ።
“ ካልሆነም ረቂቁን እኔ ልጻፍልሽ ” አላት እስክንድር፡ ዝም ስትልበት ጊዜ የቸገራት መስሎት ።
ግድ የለም ፤ እኔው እሞክራለሁ ” አለችው ፥ በሐሳቧ የምትጽፍበትን ቦታ እየመረጠች ምቹ ቦታ የለም ።
የመኝታ ክፍል ጓደኞቿ ከተኙ በኋላ፥ ሌሊት ተነሥታ የመጻፍ ሐሳብ መጣላት ።
“ ጥሩ እንግዲህ ፥ ጸፊና ሰጪኝ ። እኔ አደርስልሻ
ለሁ አላት ። ፈገግ ብላ በእሺታ ራሷን ነቀነቀች ።
እስክንድር በልቡ እየቦረቀ ትዕግሥትን መኝታ ክፍሏ ድረስ ሸኛት ። ምን ዐይነት ደብዳቤ እንደምትጽፍ ለማወቅ ልቡ ክፉኛ ጓጓ ። “ በፖስታ ታሽገው ይሆን ? ” አለ አቤል ጋ ከማድረሱ በፊት ለማንበብ አስቦ ።
ትዕግሥትን ሸኝቶ ሲመለስ ከሩቅ ስሙን የምትጠራ ሴት ሰማ ። ከመኝታ ክፍሏ መስኮት በኩል አይታው የጠራችው ቤተልሔም ነበረች ። ዘወር ብሎ ሽቅብ አያትና ለሰላምታ የጠራችው መስሎት እጁን አውለበለበ “ ቆየኝ ፡ እፈልግሃለሁ ! ” አለችው ።
ለምን ይሆን የፈለገችኝ ? ” ብሎ አሰበ ። መከረኛ ልቡ ያለ ምክንያት ሲነጥር ትሰማው ።
ፎቁን ወርዳ ድክ ድክ እያለች አጠገቡ እስክትደርስ ቆሞ ጠበቃት ።
“ ኡ ... ፍ ! ያደክማል ” አለች አጠገቡ ስትደርስ ተራራ የወጣች ያህል ቶሎ ቶሎ እየተነፈሰች በነጠላ ጫማ ስለ ነበረች፡ከእጥረቷ ጋር በማይጣጥመው ውፍረቷ ይብሱን ቁልቁል ተቀብራበት አጭር በርሜል መሰለችው ። በገጽታዋ ላይ መጠነኛ ለውጥ አስተዋል ። የተከፋች ትመስላለች የምትለውን ለመስማት ቸኮለ
አንተ ሲፈልጉህ አትገኝም" አለችው "
“ ይኸው አለው” አለ እስንድር ፍርጥም ብሎ ።
" አትቁልድ እባክህ !
“ ቀለድኩ እንዴ ? ” አለ እስክንድር በልቡ አኳኋኗ ግራ ገብቶት አኳኋኗ ሁሉ ያኮረፈች ሚስት ዐይነት ሆነበት
በዝምታ ትንሽ ቆየች ፡ ስትንደረደር እንደ መጣችው ያሰበችን በአንዴ መዘርገፍ አልቻለችም ። እጀማመሩ ቸገራት
“ እስቲ ሻይ ጋብዘኝ ?
“ ፍራንክ አለኝ ብለሽ ነው ? ! እያለ ኪሱን ዳበሰ ።
ተአምር ይፈጥር ይመስል ፥ አታዋርደኝ ኪሴ ! ” አለ ። ግን ኪሱ ባዶ መሆኑን አላጣውም።
ከሌለህ፣ ግድ የለም ፤ እኔ ልጋብዝህ
አለችው ! ጭንቀቱ ታውቋት ።
"አዎ ይሻላል ” አላት ፡ መደናገጡን ለመሸሸግ እየሞከረ « የለኝም ማለት ለምን እንደሚያሳፍረው ወይም እንደሚያስደነግጠው ለራሱም ይገርመዋል።
ግቢ ውስጥ ወደ ሚገኘው ሻይ ቤት ሄደው ትንሸ ከቆዩ በኋላ ፡ ቤትልሔም ሻይዋን ፉት እያለች ፥ ጨዋታዋን ጀመረች
“ባገኘሁህ ቁጥር እነግርሃለሁ እያልኩ” አለችና አቋረጠች ።
"ምን አላት?"
"ጓደኛዬ እንድትሆን"
የሐፍረት ሣቅ ሣቀች “ ስሜቱን ለማጥናት ዐይኖቿን ፊተ ላይ ተከለች።
ከእስክንድር አፍ ጥያቄም ሆነ መልስ አልወጣም የሚያባብሉ ዐይኖቿን ማየት አፍሮ እንገቱን ሰበረ ። የተቆጣ እንዳይመስል ግድ ፈገግ አለ ። ምን ማለት እንደ ፈለገች በውል ሊገባው አልቻለም ።
“ አየህ እስክንድር እኔ እዚህ ግቢ ውስጥ ስሜ ጠፍቷል ። ኃጢያቴ አልገባኝም ። አንተ አስተዋይ ሰው ነህ በግቢው ውስጥም ጥሩ ስም አለህ ” አለችው በአንዴ ልውጥ ብላ ፥ ጭራሽ ድምጿ ወደ ለቅሶ እያደላ ።
“እና እስክንድር የተበላሸ ስም አዳሽ ነው እንዴ ? ? አለ በልቡ ። ግልጽነቷ ግን አስገረመው ። ምርጫ ሲኖረኝ ነው ራሳችንን የምንደብቅው ። ምርጫ ማጣት ሰውን ምን ያህል ግልጽ እንደሚያደርገው ትረዳ።
“አባባልሽ በደንብ አልገባኝም ”” ኣላት አፍ አፉን ስታየው የሚናገረው ጠፍቶት
መቼም እኔ እዚህ ግቢ ውስጥ በለማ እንደምታማ ታውቃለህ ” ?
“ አሃ ! አዎ ፡ ዐልፎ ዐልፎ አንዳንድ ወሬ እሰማለሁ።አላት ፡ አጠያየቋ የሚያውቀውን ለመካድ አስቸግሮት
እንዴት እንደምትቀጥል ተቸግረች ።
“ ለመሆኑ ፥ ከአስተማሪ ጋር መውጣት ወንጀል ነው እንዴ ? "ስትል እሱኑ ጠየቀችው
“ እንደዚያ ሳይሆን፥ ግንኙነቱ ከጥቅም ጋር ስለተያያዝ ነው ። እ! እንደምታውቂው ፡ እዚህ ግቢ ውስጥ የማርክ ነገር የተማሪዉ አንገብጋቢ ጥያቄ ነው ። እንኳንስ በሌላ ግንኙነት በጭንቅላትም መብለጥ አይወድም ። እና የጥላቻው
ምንጭ ይኸ ይመስለኛል ” ሲል ፊቷ ክፉኛ ተለዋወጠ።
“ እምልሽ ፥ እኔ ተማሪዉ ሲያወራ የሰማሁትን ነው ? አለ ፡ እንዳያስቀይማት ፈርቶ ።
“ ምቀኝነት ነው ! ” አለች ፥ ሳግ እየተናነቃት ።
“እኔ ማንም ተማሪ በዚህ መንገድ ይተረጉምብኛል ብዬ አላሰብኩም ነበር። ለማንኛውም አሁን ከለማ ጋር ግኑኝነታችን ተቋርጧል።.......
💥ይቀጥላል💥
እስክንድር በልቡ እየቦረቀ ትዕግሥትን መኝታ ክፍሏ ድረስ ሸኛት ። ምን ዐይነት ደብዳቤ እንደምትጽፍ ለማወቅ ልቡ ክፉኛ ጓጓ ። “ በፖስታ ታሽገው ይሆን ? ” አለ አቤል ጋ ከማድረሱ በፊት ለማንበብ አስቦ ።
ትዕግሥትን ሸኝቶ ሲመለስ ከሩቅ ስሙን የምትጠራ ሴት ሰማ ። ከመኝታ ክፍሏ መስኮት በኩል አይታው የጠራችው ቤተልሔም ነበረች ። ዘወር ብሎ ሽቅብ አያትና ለሰላምታ የጠራችው መስሎት እጁን አውለበለበ “ ቆየኝ ፡ እፈልግሃለሁ ! ” አለችው ።
ለምን ይሆን የፈለገችኝ ? ” ብሎ አሰበ ። መከረኛ ልቡ ያለ ምክንያት ሲነጥር ትሰማው ።
ፎቁን ወርዳ ድክ ድክ እያለች አጠገቡ እስክትደርስ ቆሞ ጠበቃት ።
“ ኡ ... ፍ ! ያደክማል ” አለች አጠገቡ ስትደርስ ተራራ የወጣች ያህል ቶሎ ቶሎ እየተነፈሰች በነጠላ ጫማ ስለ ነበረች፡ከእጥረቷ ጋር በማይጣጥመው ውፍረቷ ይብሱን ቁልቁል ተቀብራበት አጭር በርሜል መሰለችው ። በገጽታዋ ላይ መጠነኛ ለውጥ አስተዋል ። የተከፋች ትመስላለች የምትለውን ለመስማት ቸኮለ
አንተ ሲፈልጉህ አትገኝም" አለችው "
“ ይኸው አለው” አለ እስንድር ፍርጥም ብሎ ።
" አትቁልድ እባክህ !
“ ቀለድኩ እንዴ ? ” አለ እስክንድር በልቡ አኳኋኗ ግራ ገብቶት አኳኋኗ ሁሉ ያኮረፈች ሚስት ዐይነት ሆነበት
በዝምታ ትንሽ ቆየች ፡ ስትንደረደር እንደ መጣችው ያሰበችን በአንዴ መዘርገፍ አልቻለችም ። እጀማመሩ ቸገራት
“ እስቲ ሻይ ጋብዘኝ ?
“ ፍራንክ አለኝ ብለሽ ነው ? ! እያለ ኪሱን ዳበሰ ።
ተአምር ይፈጥር ይመስል ፥ አታዋርደኝ ኪሴ ! ” አለ ። ግን ኪሱ ባዶ መሆኑን አላጣውም።
ከሌለህ፣ ግድ የለም ፤ እኔ ልጋብዝህ
አለችው ! ጭንቀቱ ታውቋት ።
"አዎ ይሻላል ” አላት ፡ መደናገጡን ለመሸሸግ እየሞከረ « የለኝም ማለት ለምን እንደሚያሳፍረው ወይም እንደሚያስደነግጠው ለራሱም ይገርመዋል።
ግቢ ውስጥ ወደ ሚገኘው ሻይ ቤት ሄደው ትንሸ ከቆዩ በኋላ ፡ ቤትልሔም ሻይዋን ፉት እያለች ፥ ጨዋታዋን ጀመረች
“ባገኘሁህ ቁጥር እነግርሃለሁ እያልኩ” አለችና አቋረጠች ።
"ምን አላት?"
"ጓደኛዬ እንድትሆን"
የሐፍረት ሣቅ ሣቀች “ ስሜቱን ለማጥናት ዐይኖቿን ፊተ ላይ ተከለች።
ከእስክንድር አፍ ጥያቄም ሆነ መልስ አልወጣም የሚያባብሉ ዐይኖቿን ማየት አፍሮ እንገቱን ሰበረ ። የተቆጣ እንዳይመስል ግድ ፈገግ አለ ። ምን ማለት እንደ ፈለገች በውል ሊገባው አልቻለም ።
“ አየህ እስክንድር እኔ እዚህ ግቢ ውስጥ ስሜ ጠፍቷል ። ኃጢያቴ አልገባኝም ። አንተ አስተዋይ ሰው ነህ በግቢው ውስጥም ጥሩ ስም አለህ ” አለችው በአንዴ ልውጥ ብላ ፥ ጭራሽ ድምጿ ወደ ለቅሶ እያደላ ።
“እና እስክንድር የተበላሸ ስም አዳሽ ነው እንዴ ? ? አለ በልቡ ። ግልጽነቷ ግን አስገረመው ። ምርጫ ሲኖረኝ ነው ራሳችንን የምንደብቅው ። ምርጫ ማጣት ሰውን ምን ያህል ግልጽ እንደሚያደርገው ትረዳ።
“አባባልሽ በደንብ አልገባኝም ”” ኣላት አፍ አፉን ስታየው የሚናገረው ጠፍቶት
መቼም እኔ እዚህ ግቢ ውስጥ በለማ እንደምታማ ታውቃለህ ” ?
“ አሃ ! አዎ ፡ ዐልፎ ዐልፎ አንዳንድ ወሬ እሰማለሁ።አላት ፡ አጠያየቋ የሚያውቀውን ለመካድ አስቸግሮት
እንዴት እንደምትቀጥል ተቸግረች ።
“ ለመሆኑ ፥ ከአስተማሪ ጋር መውጣት ወንጀል ነው እንዴ ? "ስትል እሱኑ ጠየቀችው
“ እንደዚያ ሳይሆን፥ ግንኙነቱ ከጥቅም ጋር ስለተያያዝ ነው ። እ! እንደምታውቂው ፡ እዚህ ግቢ ውስጥ የማርክ ነገር የተማሪዉ አንገብጋቢ ጥያቄ ነው ። እንኳንስ በሌላ ግንኙነት በጭንቅላትም መብለጥ አይወድም ። እና የጥላቻው
ምንጭ ይኸ ይመስለኛል ” ሲል ፊቷ ክፉኛ ተለዋወጠ።
“ እምልሽ ፥ እኔ ተማሪዉ ሲያወራ የሰማሁትን ነው ? አለ ፡ እንዳያስቀይማት ፈርቶ ።
“ ምቀኝነት ነው ! ” አለች ፥ ሳግ እየተናነቃት ።
“እኔ ማንም ተማሪ በዚህ መንገድ ይተረጉምብኛል ብዬ አላሰብኩም ነበር። ለማንኛውም አሁን ከለማ ጋር ግኑኝነታችን ተቋርጧል።.......
💥ይቀጥላል💥
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ትህትና ዛሬ ትንሽ ደሟ መለስ ብሎ ስትመለከት እናቷ ደስ አላት፡፡ ሰሞኑን ጥውልግልግ ብላ አስደንግጣት ነበር፡፡ ዛሬ ግን ሰውነቷን ተጣጥባ፣ ፊቷን ተቀባብታ፣ ምርጥ ለብሳ፣ ትህትናን መስላ ስታያት፤“ተመስገን” አለች በልቧ።
ያንን ምሽት እንደ አስታማሚ ልጅ ሳይሆን፤ እንደ ጥሩ አፍቃሪ ባል ፡ እቅፍ አድርጋት አደረች። ናፍቆቷን ሙሉውን ሌሊት አቅፋት በመተኛት ተወጣች፡፡
አሁን ሁሉንም ጣጣዋን ጨርሳለች፡፡ ዕቅዷን ልትፈጽም ሰዓቱ እየደረሰ ነው፡፡ በሌሊት ተነስታ ልብሷን ለባብሳ ጨረሰችና፣ ከፔርሙስ ትንሽ አጥሚት ቀድታ ካጠጣቻት በኋላ፤ “ወደ ቤት ልሂድ እማ!” ብላ ለመሄደ ተነሳች፡፡
ደግማ፤ ደጋግማ፤ ጉንጮቿን አገላብጣ ሳመቻትና፤ ወጣች፡፡ስትወጣ መንፈሷ ሁሉ ጠንካራ ነበር፡፡ ፍርሀት ጓዙን ጠቅልሎ ነው የሄደው፡፡ ቤት ደርሳ ያንን ትናንትና በፍቅር ስታሽሞነሙነው የዋለችውን የአባቷን ቅርስ ሸፋፍና፤ በቦርሳዋ ይዛ፤ ወደ መርካቶ ገሰገሰች፡፡
እዚያ እፍልሚያው ቦታ ስትደርስ ከታክሲ ወረደችና ራቅ ብላ ዓይኖቿን በሱቁ ላይ ተክላ ትጠባበቅ ጀመር፡፡
ልቧ ድው! ድው፤ ይላል፡፡ እልህና ሲቃ ይተናነቋታል፡፡ እንዷ ደቂቃ አቤት ርዝመቷ! አውሬው ወጥመዱ ውስጥ እስከሚገባ ድረስ በንቃት መጠባበቋን ቀጠለች፡፡
አንዳንድ ሱቆች መከፈት ጀምረዋል፡፡ እምብዛም ሰው አይታይም፡፡ መርካቶ ትንሽ ሞቅ ሲል እንደዚያ እንደማይተራመስ ሁሉ አሁን ያለው ሁኔታ የሚያስገርም ነው፡፡
ነጠላዋን ተሸፋፍና፣ መንገደኛ መስላ፧ አንድ ጥግ ላይ ተቀመጠችና፤ ግዳይዋን መጠባበቁን ተያያዘችው፡፡ በእርግጥም ስለቸኮለች ነው መሰል በጣም ቀድማ ነበር የመጣችው፡፡
ገንዘብ በገፍ እየገባለት የመጣው ጎረምሳ በንግዱ ላይ ትኩረቱን እየጣለ ሄዶ ነበር፡፡ አበራን ወደዚያ ካባረረ በኋላ ትርፉን ለግሉ ማግበስበስ ጀምሯል።
ገንዘብ ሲቀምሱት ይጣፍጣል፡፡ በላይ በላዩ ያስመኛል። እህል ሲጠግቡት ያስገሳል፡፡ሲበዛም ያስጠላል፡፡ ገንዘብ የሚጠግብ ሆድ ግን የለም፡፡ ግሳትም የለው፡፡ በላይ በላዩ ጨምሩልኝ፣ ጨምሩልኝ፣ የሚያሰኝ፣ እየበሉት የሚርብ ነገር ቢኖር ገንዘብ ነው፡፡
እንደሻው የራሱ የሆነውን፤ እንደፈለገው የሚያዝበትን ገንዘብ ሲያገኝ፤ እንደጠላት ገንዘብ ማውደም ሳይሆን፣ ቀስ በቀስ ሱቁን በማደራጀት ሀብታም መሆን ስለፈለገ፣ ቆጣቢና ትጉህ ሠራተኛ ሆኗል።
ዛሬ ከሌሎቹ ሁሉ ቀደም ብሎ ገበያ ሊሻማ መጣና የሱቁን በር ከፈተ፡፡ ሙሉ ጂንስ ለብሷል፡፡ ከላይ ጥቁር ክብ ባርኔጣ አድርጓል፡፡
አንገቱ ላይ አጠር ያለች ወፍራም ሻርፕ ጠምጥሞ ነበር፡፡
የሱቁን በር ከፍቶ ወደ ውስጥ መዝለቁን ስታይ ትህትና ተዘጋጀች፡፡ እሷም ጂንስ ሱሪ ነው የለበሰችው፡፡
ቀስ ብላ ቀኝ እጇን ወደ ቦርሳዋ ሰደደችና፣ ማጥበቂያውን አላላች፡፡ ሽጉጡ ላግዳጁ ዝግጁ ሆነ፡፡ አሁንም ቀስ ብላ ጨበጠቸው፡፡ እጇ የተንቀጠቀጠ መሰላት፡፡
“አይዞሽ ትህትና ጠንከር በይ” አለች ለራሷ፡፡ “የመጨረሻው ሰዓት የድል ሰዓት ደርሷል፡፡ የመጨረሻውን የድል ሰዓት ባትወጪው አበቃልሽ!” አለችና ራሷን አደፋፈረች፡፡
ይህ የመጨረሻው መክሸፍ የሌለበት እርምጃ ነው፡፡ በእውነትም ጠንከር አለች፡፡ ልቧ በትክክል መምታት ጀመረ፡፡ ሰውነቷ መራራ ደም ሲረጭ ተሰማት፡፡ የቀድሞ ባህሪዋ ከውስጧ ጥርግርግ ብሎ ወጣና፤ አዲስ የቆራጥነት፣ የደፋርነትና፤ የጭካኔ ባህሪይ ተላበሰች፡፡
“አምላኬ በደሌን አንተ ይቅር በለኝ፡፡ ነፍሴን ተቀበላት!” አለችና የሽጉጡን ምላጭ እንደያዘች እየተንደረደረች ወደ ሱቁ ሩጫዋን ቀጠለች፡፡
ሱቁ በር ላይ ስትደርስ እንደሻው በሚያየው ነገር ተደናግጦ፣ ዐይኖቹ ተበልጥጠው፣ አፉ ተከፍቶ እንደቀረ ትንፋሽ ከማውጣቱ በፊት
ሽጉጡን ላጥ አድርጋ አወጣችው፡፡
ንግግር የለ፣ ግርግር የለ፣ ፋታ ሳትሰጠው በቀጥታ እርምጃውን ወሰደች፡፡
ዷ! ዷ! ዷ! ዷ! አምስት የቆጠረች መሰላት፡፡ አራንቱን ጥይቶች ካንጣጣችበት በኋላ፣ ተንገዳግዶ መውደቁን ስታረጋግጥ፧ ሽጉጡን
ወደራሷ አዙራ አፍዋ ውስጥ አስገባቸው፡፡
ሰው መሯሯጥ ጀመረ፡፡ ለሚተራመሰው ሰው ቦታ ሳትሰጥ፤
እርምጃዋን በራሷ ላይ ወሰደች፡፡ ምላጩን ሳበቸው፡፡ ዷ! ዷ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሰማዩ የተባዘተ ጥጥ በመሰለው ደመና ተዥጐርጉሯል።
ጨረሯን የፈነጠቀችው ፀሐይ ያንን የደመና ቁልል እየናደችው ስትመጣ፤
ሰዓሊው በሸራ ላይ በብሩሹ የፈነጠቀው ንድፍ እየመሰለ ሄደ፡፡ ከዚያም ሙሉ ለሙሉ ደመናው ተገፈፈና፤ ጥርት ያለ ሰማይ ታየ፡፡
የሰው ልጅ የውስጥ ስሜቱ ሲጐዳ፣ ሲከፋው፣ ሲጨንቀው፤ ልክ ሰማዩ በደመና እንደሚያኮርፈው ሁሉ፤ ይህንን መጥፎ የውስጥ ስሜቱን በጨፈገገ ገጽታው ይገልጸዋል፡፡ በሆነ ባልሆነው ሆደ ባሻነት ያጠቃዋል፡፡
እነሆ ልቡ ከአምስት ዓመታት በላይ ከፍቅር ተገልሎ የቆየው ሻምበል ብሩክ ትህትናን ካገኘበት እለት ጀምሮ መንፈሱ ታድሶ!
የወደፊት የትዳር ህይወቱን በቅርብ ርቀት አሻግሮ መመልከት ሲጀምር፤ በእንጭጩ ተቀጨ፡፡
ትህትና ፍቅሯን ብቻ ሳይሆን፤ ያንን ደስተኛነቱን ጭምር በልቡ ውስጥ ገድላበት ነው የሄደችው፡፡
ድምጿን ለመስማት ይፈልጋል፣ ወዲያውኑ ደግሞ ከነመፈጠሯ እንዲረሳት ይመኛል፡፡ ትናፍቀዋለች፤ የሠራችው በደል ፊቱ ላይ ድቅን
ይልበታል፡፡ በቅናት ይቃጠላል፡፡ ወዲያውኑ ደግሞ ብሩኬ.... ብሩኬ....
ብሩኬ.... የሚለው ያ ለስላሳ ድምጿ፣ ያ ለስላሳ ሰውነቷ ያ ለስላሳ ባህሪዋ፤ ይታወሰዋል፡፡
በፊት የነበረችው ትህትና እንዴት የምትወደድ ልጅ ነበረች? ለምን ፈጣሪ አሳይቶ ነሳው? ምነው እሱ ለፍቅር አልታደለ? ሁል ጊዜ መጨነቅ?
“ምነው የዚያን ዕለት ባልተገናኘን ኖሮ” የሚል ሃሣብ መጣበት፡፡ ሆኖም በመገናኘታቸው አንድ መልካም ሥራ መስራቱ ያስደስተዋል፡፡
አጋር ያልነበራት እናቷን መርዳት መቻሉ እርካታን ይሰጠዋል።
ጽድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም
ከክፋት ደግነት ሳይሻል አይቀርም፡፡ እንዲሉ፣ እሷ ትበድለው እንጂ፤ እሱ ከበደል ይልቅ መልካም ሥራን የሠራ ተበዳይ መሆኑ ሲታወሰው፤ “ይሁን እስቲ ሁሉ ነገር ከፈጣሪ ይገኛል” ይልና
ይጽናናል፡፡
እንደ እውነቱ ከሆነ የሰሞኑ ሁኔታው የተለየ ነበር፡፡ ናፍቆቷ ነፍሱን ሊያወጣው ደርሷል፡፡
በውስጡ ፍቅርና ጥላቻ ነግሰውበታል፡፡ እንዳይጠላት ይወዳታል፣ እንዳይወዳት ደግሞ የሠራችው ሥራ...እንዳንድ ጊዜ ያ አለቃቀሷ፤ እዚያ እላዩ ላይ ተጠምጥማ እየተንሰቀሰቀች የተናገረችው ንግግር፣ ትዝ ይለውና፤ “ምን ነበረበት ይቅር ብላት ኖሮ? ግብዝ ነኝ” በማለት እራሱን
ይኮንናል፡፡ ወዲያው ደግሞ የሻክረና ጥርጣሬ የገባው ልብ ተመልሶ ልብ
ላይሆን፡፡ የነቃ ብርሌ ተመልሶ ዕቃ ላይሆን፣ አጉል ሙጥኝ አለማለቱን
ይወደውና..
እንኳንም በጊዜ አቋረጥን” የሚል ስሜት ይሰማዋል፡፡በጠዋቱ መ/ቤቱ እንደደረሰ ወደ ቢሮ ከመግባቱ በፊት ጫማውን
ሊያስጠርግ ሄደ፡፡ሰማዩን አየው፡፡ ከቤት ሲወጣ በደመና የተሸፈነ ነበር፡፡ አሁን
ግን ጥርት ብሏል፡፡ የሱ ስሜት ግን እንደሰማዩ አልጠራም፡፡ ፊቱ ጨፍግጓል፡፡ ጫማውን አስጠርጐ ወደ መሥሪያ ቤቱ ግቢ ሲዘልቅ......
“እንደምን አደርክ ሻምበል መልዕክት አለህ” አዳሪው ፖሊስ ከኪሱ ውስጥ ያስቀመጠውን ፖስታ አቀበለው፡፡
ሻምበል ፖስታውን ተቀብሎ ተመለከተው፡፡ የላኪው ሥም
የለበትም፡፡
የአደራ ደብዳቤነቱን እንጂ ከማን እንደተላከ አይገልጽም፡፡
“ማን ነው የሰጠህ?” ሲል ፖሊሱን ጠየቀው፡፡ ስሟን እንዳልነገረችው ገለፀለት፡፡ በቀጥታ ወደ ቢሮው ሄደ፡፡
የቢሮውን መስኮት ከፈተው፡፡ ንፁህ አየር ገባ፡፡ ከዚያም
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አምስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ትህትና ዛሬ ትንሽ ደሟ መለስ ብሎ ስትመለከት እናቷ ደስ አላት፡፡ ሰሞኑን ጥውልግልግ ብላ አስደንግጣት ነበር፡፡ ዛሬ ግን ሰውነቷን ተጣጥባ፣ ፊቷን ተቀባብታ፣ ምርጥ ለብሳ፣ ትህትናን መስላ ስታያት፤“ተመስገን” አለች በልቧ።
ያንን ምሽት እንደ አስታማሚ ልጅ ሳይሆን፤ እንደ ጥሩ አፍቃሪ ባል ፡ እቅፍ አድርጋት አደረች። ናፍቆቷን ሙሉውን ሌሊት አቅፋት በመተኛት ተወጣች፡፡
አሁን ሁሉንም ጣጣዋን ጨርሳለች፡፡ ዕቅዷን ልትፈጽም ሰዓቱ እየደረሰ ነው፡፡ በሌሊት ተነስታ ልብሷን ለባብሳ ጨረሰችና፣ ከፔርሙስ ትንሽ አጥሚት ቀድታ ካጠጣቻት በኋላ፤ “ወደ ቤት ልሂድ እማ!” ብላ ለመሄደ ተነሳች፡፡
ደግማ፤ ደጋግማ፤ ጉንጮቿን አገላብጣ ሳመቻትና፤ ወጣች፡፡ስትወጣ መንፈሷ ሁሉ ጠንካራ ነበር፡፡ ፍርሀት ጓዙን ጠቅልሎ ነው የሄደው፡፡ ቤት ደርሳ ያንን ትናንትና በፍቅር ስታሽሞነሙነው የዋለችውን የአባቷን ቅርስ ሸፋፍና፤ በቦርሳዋ ይዛ፤ ወደ መርካቶ ገሰገሰች፡፡
እዚያ እፍልሚያው ቦታ ስትደርስ ከታክሲ ወረደችና ራቅ ብላ ዓይኖቿን በሱቁ ላይ ተክላ ትጠባበቅ ጀመር፡፡
ልቧ ድው! ድው፤ ይላል፡፡ እልህና ሲቃ ይተናነቋታል፡፡ እንዷ ደቂቃ አቤት ርዝመቷ! አውሬው ወጥመዱ ውስጥ እስከሚገባ ድረስ በንቃት መጠባበቋን ቀጠለች፡፡
አንዳንድ ሱቆች መከፈት ጀምረዋል፡፡ እምብዛም ሰው አይታይም፡፡ መርካቶ ትንሽ ሞቅ ሲል እንደዚያ እንደማይተራመስ ሁሉ አሁን ያለው ሁኔታ የሚያስገርም ነው፡፡
ነጠላዋን ተሸፋፍና፣ መንገደኛ መስላ፧ አንድ ጥግ ላይ ተቀመጠችና፤ ግዳይዋን መጠባበቁን ተያያዘችው፡፡ በእርግጥም ስለቸኮለች ነው መሰል በጣም ቀድማ ነበር የመጣችው፡፡
ገንዘብ በገፍ እየገባለት የመጣው ጎረምሳ በንግዱ ላይ ትኩረቱን እየጣለ ሄዶ ነበር፡፡ አበራን ወደዚያ ካባረረ በኋላ ትርፉን ለግሉ ማግበስበስ ጀምሯል።
ገንዘብ ሲቀምሱት ይጣፍጣል፡፡ በላይ በላዩ ያስመኛል። እህል ሲጠግቡት ያስገሳል፡፡ሲበዛም ያስጠላል፡፡ ገንዘብ የሚጠግብ ሆድ ግን የለም፡፡ ግሳትም የለው፡፡ በላይ በላዩ ጨምሩልኝ፣ ጨምሩልኝ፣ የሚያሰኝ፣ እየበሉት የሚርብ ነገር ቢኖር ገንዘብ ነው፡፡
እንደሻው የራሱ የሆነውን፤ እንደፈለገው የሚያዝበትን ገንዘብ ሲያገኝ፤ እንደጠላት ገንዘብ ማውደም ሳይሆን፣ ቀስ በቀስ ሱቁን በማደራጀት ሀብታም መሆን ስለፈለገ፣ ቆጣቢና ትጉህ ሠራተኛ ሆኗል።
ዛሬ ከሌሎቹ ሁሉ ቀደም ብሎ ገበያ ሊሻማ መጣና የሱቁን በር ከፈተ፡፡ ሙሉ ጂንስ ለብሷል፡፡ ከላይ ጥቁር ክብ ባርኔጣ አድርጓል፡፡
አንገቱ ላይ አጠር ያለች ወፍራም ሻርፕ ጠምጥሞ ነበር፡፡
የሱቁን በር ከፍቶ ወደ ውስጥ መዝለቁን ስታይ ትህትና ተዘጋጀች፡፡ እሷም ጂንስ ሱሪ ነው የለበሰችው፡፡
ቀስ ብላ ቀኝ እጇን ወደ ቦርሳዋ ሰደደችና፣ ማጥበቂያውን አላላች፡፡ ሽጉጡ ላግዳጁ ዝግጁ ሆነ፡፡ አሁንም ቀስ ብላ ጨበጠቸው፡፡ እጇ የተንቀጠቀጠ መሰላት፡፡
“አይዞሽ ትህትና ጠንከር በይ” አለች ለራሷ፡፡ “የመጨረሻው ሰዓት የድል ሰዓት ደርሷል፡፡ የመጨረሻውን የድል ሰዓት ባትወጪው አበቃልሽ!” አለችና ራሷን አደፋፈረች፡፡
ይህ የመጨረሻው መክሸፍ የሌለበት እርምጃ ነው፡፡ በእውነትም ጠንከር አለች፡፡ ልቧ በትክክል መምታት ጀመረ፡፡ ሰውነቷ መራራ ደም ሲረጭ ተሰማት፡፡ የቀድሞ ባህሪዋ ከውስጧ ጥርግርግ ብሎ ወጣና፤ አዲስ የቆራጥነት፣ የደፋርነትና፤ የጭካኔ ባህሪይ ተላበሰች፡፡
“አምላኬ በደሌን አንተ ይቅር በለኝ፡፡ ነፍሴን ተቀበላት!” አለችና የሽጉጡን ምላጭ እንደያዘች እየተንደረደረች ወደ ሱቁ ሩጫዋን ቀጠለች፡፡
ሱቁ በር ላይ ስትደርስ እንደሻው በሚያየው ነገር ተደናግጦ፣ ዐይኖቹ ተበልጥጠው፣ አፉ ተከፍቶ እንደቀረ ትንፋሽ ከማውጣቱ በፊት
ሽጉጡን ላጥ አድርጋ አወጣችው፡፡
ንግግር የለ፣ ግርግር የለ፣ ፋታ ሳትሰጠው በቀጥታ እርምጃውን ወሰደች፡፡
ዷ! ዷ! ዷ! ዷ! አምስት የቆጠረች መሰላት፡፡ አራንቱን ጥይቶች ካንጣጣችበት በኋላ፣ ተንገዳግዶ መውደቁን ስታረጋግጥ፧ ሽጉጡን
ወደራሷ አዙራ አፍዋ ውስጥ አስገባቸው፡፡
ሰው መሯሯጥ ጀመረ፡፡ ለሚተራመሰው ሰው ቦታ ሳትሰጥ፤
እርምጃዋን በራሷ ላይ ወሰደች፡፡ ምላጩን ሳበቸው፡፡ ዷ! ዷ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሰማዩ የተባዘተ ጥጥ በመሰለው ደመና ተዥጐርጉሯል።
ጨረሯን የፈነጠቀችው ፀሐይ ያንን የደመና ቁልል እየናደችው ስትመጣ፤
ሰዓሊው በሸራ ላይ በብሩሹ የፈነጠቀው ንድፍ እየመሰለ ሄደ፡፡ ከዚያም ሙሉ ለሙሉ ደመናው ተገፈፈና፤ ጥርት ያለ ሰማይ ታየ፡፡
የሰው ልጅ የውስጥ ስሜቱ ሲጐዳ፣ ሲከፋው፣ ሲጨንቀው፤ ልክ ሰማዩ በደመና እንደሚያኮርፈው ሁሉ፤ ይህንን መጥፎ የውስጥ ስሜቱን በጨፈገገ ገጽታው ይገልጸዋል፡፡ በሆነ ባልሆነው ሆደ ባሻነት ያጠቃዋል፡፡
እነሆ ልቡ ከአምስት ዓመታት በላይ ከፍቅር ተገልሎ የቆየው ሻምበል ብሩክ ትህትናን ካገኘበት እለት ጀምሮ መንፈሱ ታድሶ!
የወደፊት የትዳር ህይወቱን በቅርብ ርቀት አሻግሮ መመልከት ሲጀምር፤ በእንጭጩ ተቀጨ፡፡
ትህትና ፍቅሯን ብቻ ሳይሆን፤ ያንን ደስተኛነቱን ጭምር በልቡ ውስጥ ገድላበት ነው የሄደችው፡፡
ድምጿን ለመስማት ይፈልጋል፣ ወዲያውኑ ደግሞ ከነመፈጠሯ እንዲረሳት ይመኛል፡፡ ትናፍቀዋለች፤ የሠራችው በደል ፊቱ ላይ ድቅን
ይልበታል፡፡ በቅናት ይቃጠላል፡፡ ወዲያውኑ ደግሞ ብሩኬ.... ብሩኬ....
ብሩኬ.... የሚለው ያ ለስላሳ ድምጿ፣ ያ ለስላሳ ሰውነቷ ያ ለስላሳ ባህሪዋ፤ ይታወሰዋል፡፡
በፊት የነበረችው ትህትና እንዴት የምትወደድ ልጅ ነበረች? ለምን ፈጣሪ አሳይቶ ነሳው? ምነው እሱ ለፍቅር አልታደለ? ሁል ጊዜ መጨነቅ?
“ምነው የዚያን ዕለት ባልተገናኘን ኖሮ” የሚል ሃሣብ መጣበት፡፡ ሆኖም በመገናኘታቸው አንድ መልካም ሥራ መስራቱ ያስደስተዋል፡፡
አጋር ያልነበራት እናቷን መርዳት መቻሉ እርካታን ይሰጠዋል።
ጽድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም
ከክፋት ደግነት ሳይሻል አይቀርም፡፡ እንዲሉ፣ እሷ ትበድለው እንጂ፤ እሱ ከበደል ይልቅ መልካም ሥራን የሠራ ተበዳይ መሆኑ ሲታወሰው፤ “ይሁን እስቲ ሁሉ ነገር ከፈጣሪ ይገኛል” ይልና
ይጽናናል፡፡
እንደ እውነቱ ከሆነ የሰሞኑ ሁኔታው የተለየ ነበር፡፡ ናፍቆቷ ነፍሱን ሊያወጣው ደርሷል፡፡
በውስጡ ፍቅርና ጥላቻ ነግሰውበታል፡፡ እንዳይጠላት ይወዳታል፣ እንዳይወዳት ደግሞ የሠራችው ሥራ...እንዳንድ ጊዜ ያ አለቃቀሷ፤ እዚያ እላዩ ላይ ተጠምጥማ እየተንሰቀሰቀች የተናገረችው ንግግር፣ ትዝ ይለውና፤ “ምን ነበረበት ይቅር ብላት ኖሮ? ግብዝ ነኝ” በማለት እራሱን
ይኮንናል፡፡ ወዲያው ደግሞ የሻክረና ጥርጣሬ የገባው ልብ ተመልሶ ልብ
ላይሆን፡፡ የነቃ ብርሌ ተመልሶ ዕቃ ላይሆን፣ አጉል ሙጥኝ አለማለቱን
ይወደውና..
እንኳንም በጊዜ አቋረጥን” የሚል ስሜት ይሰማዋል፡፡በጠዋቱ መ/ቤቱ እንደደረሰ ወደ ቢሮ ከመግባቱ በፊት ጫማውን
ሊያስጠርግ ሄደ፡፡ሰማዩን አየው፡፡ ከቤት ሲወጣ በደመና የተሸፈነ ነበር፡፡ አሁን
ግን ጥርት ብሏል፡፡ የሱ ስሜት ግን እንደሰማዩ አልጠራም፡፡ ፊቱ ጨፍግጓል፡፡ ጫማውን አስጠርጐ ወደ መሥሪያ ቤቱ ግቢ ሲዘልቅ......
“እንደምን አደርክ ሻምበል መልዕክት አለህ” አዳሪው ፖሊስ ከኪሱ ውስጥ ያስቀመጠውን ፖስታ አቀበለው፡፡
ሻምበል ፖስታውን ተቀብሎ ተመለከተው፡፡ የላኪው ሥም
የለበትም፡፡
የአደራ ደብዳቤነቱን እንጂ ከማን እንደተላከ አይገልጽም፡፡
“ማን ነው የሰጠህ?” ሲል ፖሊሱን ጠየቀው፡፡ ስሟን እንዳልነገረችው ገለፀለት፡፡ በቀጥታ ወደ ቢሮው ሄደ፡፡
የቢሮውን መስኮት ከፈተው፡፡ ንፁህ አየር ገባ፡፡ ከዚያም
👍1
መለዮውን አውልቆ፤ ጠረጴዛው ላይ ካኖረው በኋላ፤
የዚህን እንግዳ የሆነ ደብዳቤ ይዘት ለማወቅ ጓጉቶ፤ ፓስታውን ቀደደው፡፡
“እንደምን አደርክ ሻምበል ገብተሃል እንዴ?” የጣቢያው አዛዥ ወደ ቢሮአችው ሲሄዱ እግረ መንገዳቸውን ሰላምታ ሰጥተውት አለፉ፡፡
እግዚአብሔር ይመስግን ሻለቃ ደህና አደሩ?” አፀፋውን ቆሞ ሰላምታ ከሰጠ በኋላ ወደ ደብዳቤው ተመለሰ፡፡
ሻምበል ብሩክ ደብዳቤውን ማንበብ ሲጀምር ሰውነቱ እየተለዋወጠ ሄደ፡፡ ቀስ በቀስ ልቡ ታርዶ እንደተጣለ ዶሮ ትንደፋደፍ ጀመር፡፡ በመደናገርና በድንጋጤ ስሜት እንደተዋጠ ንባቡን ቀጠለ፡፡ ወደ ዝርዝሩ በገባ ቁጥር ደርዘን ፍርሃትና ጥርጣሬ እየተጫነው ሄደ።
ይህ ጭንቀቱ በግንባሩ ላይ ላብ ችፍ፤ ችፍ፤ ያስደርገው ጀመር፡፡ ከዚያም የሆነ ቦታ ላይ ሲደርስ ወረቀቱን አጥፎ ዐይኖቹን ጨፈነና..
“እፎ ይ ይ ይ ......” ሲል በረጅሙ ተነፈሰ፡፡ ልቡ ትር ትር ትር አለች፡፡ “ወይኔ ብሩክ ምን ተአምር ነው የማየው? ወይኔ የበላይ ልጅ፤ ነፍሰ ገዳይ ልሆን ነው ማለት ነው?
እውነት ትህትና ጨክና እራሷን በራሷ ልታጠፋ ነው ማለት ነው?”
እናቷ ሆስፒታል ውስጥ እያለቀሰች ታየችው፡፡ ወንድሟ አንዱአለም ፊቱ ላይ ድቅን አለበት፡፡
“አንተ ነፍስ ገዳይ እህቴን ገደልካት” ብሎ ጣቱን ሲቀስርበት ታየው። ዝቅ እያለ ሄደ። ኸረ በፈጣሪ? አገር ጥላ ኮበለለች? ትህትና እራሷን አታጠፋም! ባይሆን ወደ አንድ የማይታወቅ ቦታ ሄዳለች ማለት
እንደሻው? እንደሻው? የዚያን ጊዜ አንገቱ ላይ ተጠምጥማ እያለቀሰች የነገረችው ትዝ አለው፡፡ ልክ ነበር ማለት ነው? ትህትና አልዋሸችኝም ነበር ማለት ነው?
ወይኔ ብሩክ ጥይት ተኩሼ ባልገድላትም ገዳይዋ እኔው ነኝ፡፡ ወረደ ልክ ነው፡፡ ወደ መጨረሻው ሲቃረብ በጭንቅላቱ ወስጥ የሆነ ነገር የፈነዳ መሰለው፡፡ አይኖቹን
ጨፈነና ትንሽ ቆይቶ ገለጣቸው፡ አልቀረለትም :: የጠረጠረው ሆኖ አገኘው፡፡
ስሜቱ ተናወጠ፡፡ አእምሮው በጭንቀት ሊፈርስ ተቃረበ፡፡ ዐይኖቹን አሁንም ጨፈነ፡፡ እንደገና ገለጣቸው፡፡ እንደገና ጨፈናቸው...
እንደገና በመጨረሻው ብዥ ብዥ ብዥ... የሚል ነገር ታየው፡፡ አስፈሪው የስንብት ቃል! ሲያነበው እያንዳንዱ ፊደል ጦር ሆኖ አእምሮውን አየሰቀሳቀ፤ እየወጋ፤ አቆሰለው፡፡ የዚያች የንፁህ ልጅ
የስንብት ቃል......
“እወድሃለሁ ብሩኬ፡፡ የመጀመሪያም የመጨረሻም ፍቅሬ አንተ ነበርክ፡፡ ደህና ሁንልኝ....”
“ሁሉ ነገር አልቋል መርካቶ
“ወይኔ ብሩክ!” እንደ እብድ ወንበሩን ወደዚያ አሸቀንጥሮ ወደ አለቃው ቢሮ ሮጠ፡፡
“እባክዎትን ሻለቃ አንድ ጊዜ የመኪና ቁልፍ ይስጡኝ?” ሰውነቱ
ይንቀጠቀጥ ነበር፡፡
ሻለቃ ሁኔታውን ሲያዩ ደነገጡ፡፡ያልተለመደ ሆኔታ ይታይበት
ነበር፡፡ “ምን ሆነሃል ሻምበል? አይዞህ ረጋ በል” ከወንበራቸው ተነስተው፡፡ ድምፁም ልክ እንደሰውነቱ ይንቀጠቀጥ ነበር።
የሱን ሀኔታ ሲያዩ ሻለቃ ሃሣባቸውን አስተካከሉ፡፡ በዚህ ሁኔታ መኪና ይዞ ቢሄድ አደጋ እንዳይደርስበት ስለፈሩ የአሥር አለቃ ዓለማየሁን ጠርተው ......
“እንካ ቁልፍ፡፡ ሻምበልን የሚፈልገው ቦታ አድርሰው፡፡ ረጋ ብላችሁ ሂዱ ታዲያ! " ሲሉ ትዕዛዝ ሰጡት፡፡ ከዚያም ወደ መርካቶ ይከንፉ ጀመር፡፡
ሻምበል ብሩክ ሩጫው ከንቱ ... ጥረቱ ዜሮ የምትወደው ጓደኛው ትህትና... ጀንበሯ ጠለቀች? ወይስ?
እየበረሩ መርካቶ ገበያ አዳራሽ አጠገብ በህዝብ የተጨናነቀ ስፍራ ደረሱ::
“ቱፍ! ቱፍ! በሞትኩት እኔን! እኔን!
ወይኔ ምን ብታደርገው ነው? ያቺን አበባ የመሰለች ልጅ?.....”
“አቤት! አቤት! እንዴት ያለው አሳዛኝ ታሪክ ነው? አሁን ይሄ የሰይጣን እንጂ ፤ የሰው ሥራ ይሉታል? የጋኔን ስራ እንጂ! ያንተ ያለህ ድብን አድርጓት ለራሱም ጠጣው አቤት! አቤት!”
ግማሹ ከንፈሩን ይመጣል፣ ገሚሱ ደረቱን ይደልቃል፡፡ ወደ ስማይ ወደ ፈጣሪ እያንጋጠጠ....
“ወንድ ነው! እኔ በበኩሌ አደንቀዋለሁ!! አንጀቱን አሳርራው ይሆናል ዋጋዋን የሰጣት! በቁሙ ተቃጥሎ ከሚሞት፤
አቃጥሏት መገላገሉ በጀው”፡፡ የጉርምስና ስሜት ከሚታይባቸው መካከል
የሚሰነዘር.... እንደዚያ ሰው ተሰብስቦ የሚንጫጫበትን እየሰነጠቀች አንዲት የፓሊስ ሠሌዳ ቁጥር ያላት ቮልስ ዋገን መሀል ገብታ ቆመች፡፡ ሻምበል ብሩክ ፊቱ ጥላሸት መስሎ፣ ዐይኖቹ በድንጋጤ
እንደተጐለጐሉ፤ ከመኪናው ላይ ዱብ ብሎ ወረደ፡፡ አብዛኞቹ በፍርሃት
ገለል ገለል አሉ፡፡ የሚታፈሱ ነው የመሰላቸው፡፡
“ምን የተፈጠረ ነገር አለ? ምንድ ነው!” አንዱን ጐረምሣ ቢጤ አፋጠጠው፡፡
ለሱ አልታወቀውም እንጂ ልጁን እንደ ነፍሰ ገዳይ ኮሌታውን ጨምድዶ ይዞት ነበር፡፡
“ተጋደሉ በጥይት ወንፊት አደረጋት” አንገቱን ለማስለቀቅ እየሞከረ፡፡
“ማን ነው ማንን ወንፊት ያደረገው?” ተገላቢጦሹ ግራ ገባው።
“አትቀባጥር! ቀባጣሪ! ለወሬ ከመሽቀዳደምህ በፊት አጣራ!
ወሬኛ!” አለና አንዱ ጎረምሣ ልጁን ወደዚያ ገፍትሮ ወደ ሻምበል ብሩክ
ጠጋ አለ፡፡
“ጌታዬ እሷ ናት የመታችው፡፡ ደጋግማ ከተኮሰችበት በኋላ ለራሷ ጠጣች፡፡ በጣም የሚያሳዝን ነገር ነው፡፡ ይህን በዐይኔ በብረቱ ነው ያየሁት” አለና ምስክርነቱን ሰጠ፡፡
“ሞታለች?” ሻምበል ስውነቱ በብርክ እየተንቀጠቀጠ፡፡ ትሙት ትኑር አላውቅም፡፡ ከዚህ ወደ ሆስፒታል ሲወሰዱ ግን ሁለቱም በህይወት ነበሩ፡፡ የሚተርፉ ግን አይመስለኝም፡፡”
“የት ሆስፒታል ነው የተወሰዱት? ና እስቲ ግባ” ልጁን መኪና ውስጥ አስገባው፡፡ሁለቱም ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል መወሰዳቸው ተነገረውና፤ ተያይዘው ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በረሩ፡፡ሻምበል ብሩክ ነፍሱን አያውቅም፡፡ ሆስፒታል ደርሰው ወዲያና ወዲህ እየተራወጡ ስለ ሁኔታው ጠየቁ፡፡
አንዲት ነጭ ካፖርት የለበሰች ነርስ የሆነውን ቀስ ብላ አስረዳችው፡፡ ሁለቱም ጉዳተኞች በህይወት እንደሚገኙና በድንገተኛ ህክምና ክፍል እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ረጋ ብላ ገለፀችለት፡፡
“እውነትሽን ነው? አልሞተችም?” በሁለት እጆቹ ትከሻዋን ይዞ በጉጉት ጠየቃት፡፡
ይመኑኝ በተለይ እሷ ለህይወቷ የሚያሰጋ ጉዳት እንዳልደረሰባት ሀኪሞቹ ሲናገሩ በጆሮዬ ሰምቻለሁ፡፡” . ነፍሱን ትንሽ
መለስ አደረገችለት፡፡
“ምን እናድርግ አሁን ሲስተር? ደም የሚጠየቅ ከሆነ እባክሽን አጣሪልኝና
ደም ልስጥ፡፡ ሌላም የሚያስፈልገውን እርዳታ ሁሉ አሳውቂኝ፡፡ ሲስተር ትልቅ ባለውለታዬ ትሆኛለሽ፡፡ ተባበሪኝ” ተማፀናት፡፡
“ግድ የለዎትም አይረበሹ፡፡ የሚሆነውን ሁሉ በዶክተሮች ትዕዛዝ መሠረት እንፈጽማለን፡፡ እስከዚያው ይምጡ” አለችና ወስዳ አንድ ክፍል ውስጥ አረፍ እንዲል አደረገችው፡፡
ሁኔታው ስላሳዘናት ነው ትንሽ እረፍት እንዲወስድና፤ እራሱን እንዲያረጋጋ፤ የፈለገችው፡፡
ሻምበል ብሩክ አምላክ ነፍስ ገዳይ እንዳያደርገው በልቡ ፀሎት እያደረሰ፣ የሚሆነውን ሁሉ በሲስተር ማን አህሎች በኩል ለመሰማት በጉጉት መጠባበቁን ቀጠለ፡፡
“መኪናውን ይዘህ ሂድ” አለና ሾፌሩን ሸኘው፡፡ ለልጁ አምስት ብር አስጨብጦ ሁለቱንም ላክና፤ እሱ እዚያ ሆኖ ውጤቱን ይጠባበቅ ጀመር፡፡ አሁን ትንሽ ነፍሱ መለስ ስትልለት፤ አንድ ነገር ትዝ አለው፡፡
ለአዜብ እንዲደውልላት አደራ ብላው ነበር፡፡ የስልክ ቁጥሩን ከደብዳቤው ላይ አነበበና ለአዜብ ደወለላት፡፡ ዝም ብሎ በደፈናው ችግር መድረሱን ገልጾ፤
ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በአስቸኳይ እንድትመጣ ነገራት፡፡
አዜብ ይህንን ስትሰማ ክው ብላ ደንገጠች፡፡ አንዱአለም የሞተ መሰላት፡፡ ነፍሷን ሳታውቀው፤ ፀጉሯን እንኳን ሳታበጥር፤ እየከነፈች መጣች፡፡ ሻምበል ብሩክ በሩ ላይ ሆኖ
የዚህን እንግዳ የሆነ ደብዳቤ ይዘት ለማወቅ ጓጉቶ፤ ፓስታውን ቀደደው፡፡
“እንደምን አደርክ ሻምበል ገብተሃል እንዴ?” የጣቢያው አዛዥ ወደ ቢሮአችው ሲሄዱ እግረ መንገዳቸውን ሰላምታ ሰጥተውት አለፉ፡፡
እግዚአብሔር ይመስግን ሻለቃ ደህና አደሩ?” አፀፋውን ቆሞ ሰላምታ ከሰጠ በኋላ ወደ ደብዳቤው ተመለሰ፡፡
ሻምበል ብሩክ ደብዳቤውን ማንበብ ሲጀምር ሰውነቱ እየተለዋወጠ ሄደ፡፡ ቀስ በቀስ ልቡ ታርዶ እንደተጣለ ዶሮ ትንደፋደፍ ጀመር፡፡ በመደናገርና በድንጋጤ ስሜት እንደተዋጠ ንባቡን ቀጠለ፡፡ ወደ ዝርዝሩ በገባ ቁጥር ደርዘን ፍርሃትና ጥርጣሬ እየተጫነው ሄደ።
ይህ ጭንቀቱ በግንባሩ ላይ ላብ ችፍ፤ ችፍ፤ ያስደርገው ጀመር፡፡ ከዚያም የሆነ ቦታ ላይ ሲደርስ ወረቀቱን አጥፎ ዐይኖቹን ጨፈነና..
“እፎ ይ ይ ይ ......” ሲል በረጅሙ ተነፈሰ፡፡ ልቡ ትር ትር ትር አለች፡፡ “ወይኔ ብሩክ ምን ተአምር ነው የማየው? ወይኔ የበላይ ልጅ፤ ነፍሰ ገዳይ ልሆን ነው ማለት ነው?
እውነት ትህትና ጨክና እራሷን በራሷ ልታጠፋ ነው ማለት ነው?”
እናቷ ሆስፒታል ውስጥ እያለቀሰች ታየችው፡፡ ወንድሟ አንዱአለም ፊቱ ላይ ድቅን አለበት፡፡
“አንተ ነፍስ ገዳይ እህቴን ገደልካት” ብሎ ጣቱን ሲቀስርበት ታየው። ዝቅ እያለ ሄደ። ኸረ በፈጣሪ? አገር ጥላ ኮበለለች? ትህትና እራሷን አታጠፋም! ባይሆን ወደ አንድ የማይታወቅ ቦታ ሄዳለች ማለት
እንደሻው? እንደሻው? የዚያን ጊዜ አንገቱ ላይ ተጠምጥማ እያለቀሰች የነገረችው ትዝ አለው፡፡ ልክ ነበር ማለት ነው? ትህትና አልዋሸችኝም ነበር ማለት ነው?
ወይኔ ብሩክ ጥይት ተኩሼ ባልገድላትም ገዳይዋ እኔው ነኝ፡፡ ወረደ ልክ ነው፡፡ ወደ መጨረሻው ሲቃረብ በጭንቅላቱ ወስጥ የሆነ ነገር የፈነዳ መሰለው፡፡ አይኖቹን
ጨፈነና ትንሽ ቆይቶ ገለጣቸው፡ አልቀረለትም :: የጠረጠረው ሆኖ አገኘው፡፡
ስሜቱ ተናወጠ፡፡ አእምሮው በጭንቀት ሊፈርስ ተቃረበ፡፡ ዐይኖቹን አሁንም ጨፈነ፡፡ እንደገና ገለጣቸው፡፡ እንደገና ጨፈናቸው...
እንደገና በመጨረሻው ብዥ ብዥ ብዥ... የሚል ነገር ታየው፡፡ አስፈሪው የስንብት ቃል! ሲያነበው እያንዳንዱ ፊደል ጦር ሆኖ አእምሮውን አየሰቀሳቀ፤ እየወጋ፤ አቆሰለው፡፡ የዚያች የንፁህ ልጅ
የስንብት ቃል......
“እወድሃለሁ ብሩኬ፡፡ የመጀመሪያም የመጨረሻም ፍቅሬ አንተ ነበርክ፡፡ ደህና ሁንልኝ....”
“ሁሉ ነገር አልቋል መርካቶ
“ወይኔ ብሩክ!” እንደ እብድ ወንበሩን ወደዚያ አሸቀንጥሮ ወደ አለቃው ቢሮ ሮጠ፡፡
“እባክዎትን ሻለቃ አንድ ጊዜ የመኪና ቁልፍ ይስጡኝ?” ሰውነቱ
ይንቀጠቀጥ ነበር፡፡
ሻለቃ ሁኔታውን ሲያዩ ደነገጡ፡፡ያልተለመደ ሆኔታ ይታይበት
ነበር፡፡ “ምን ሆነሃል ሻምበል? አይዞህ ረጋ በል” ከወንበራቸው ተነስተው፡፡ ድምፁም ልክ እንደሰውነቱ ይንቀጠቀጥ ነበር።
የሱን ሀኔታ ሲያዩ ሻለቃ ሃሣባቸውን አስተካከሉ፡፡ በዚህ ሁኔታ መኪና ይዞ ቢሄድ አደጋ እንዳይደርስበት ስለፈሩ የአሥር አለቃ ዓለማየሁን ጠርተው ......
“እንካ ቁልፍ፡፡ ሻምበልን የሚፈልገው ቦታ አድርሰው፡፡ ረጋ ብላችሁ ሂዱ ታዲያ! " ሲሉ ትዕዛዝ ሰጡት፡፡ ከዚያም ወደ መርካቶ ይከንፉ ጀመር፡፡
ሻምበል ብሩክ ሩጫው ከንቱ ... ጥረቱ ዜሮ የምትወደው ጓደኛው ትህትና... ጀንበሯ ጠለቀች? ወይስ?
እየበረሩ መርካቶ ገበያ አዳራሽ አጠገብ በህዝብ የተጨናነቀ ስፍራ ደረሱ::
“ቱፍ! ቱፍ! በሞትኩት እኔን! እኔን!
ወይኔ ምን ብታደርገው ነው? ያቺን አበባ የመሰለች ልጅ?.....”
“አቤት! አቤት! እንዴት ያለው አሳዛኝ ታሪክ ነው? አሁን ይሄ የሰይጣን እንጂ ፤ የሰው ሥራ ይሉታል? የጋኔን ስራ እንጂ! ያንተ ያለህ ድብን አድርጓት ለራሱም ጠጣው አቤት! አቤት!”
ግማሹ ከንፈሩን ይመጣል፣ ገሚሱ ደረቱን ይደልቃል፡፡ ወደ ስማይ ወደ ፈጣሪ እያንጋጠጠ....
“ወንድ ነው! እኔ በበኩሌ አደንቀዋለሁ!! አንጀቱን አሳርራው ይሆናል ዋጋዋን የሰጣት! በቁሙ ተቃጥሎ ከሚሞት፤
አቃጥሏት መገላገሉ በጀው”፡፡ የጉርምስና ስሜት ከሚታይባቸው መካከል
የሚሰነዘር.... እንደዚያ ሰው ተሰብስቦ የሚንጫጫበትን እየሰነጠቀች አንዲት የፓሊስ ሠሌዳ ቁጥር ያላት ቮልስ ዋገን መሀል ገብታ ቆመች፡፡ ሻምበል ብሩክ ፊቱ ጥላሸት መስሎ፣ ዐይኖቹ በድንጋጤ
እንደተጐለጐሉ፤ ከመኪናው ላይ ዱብ ብሎ ወረደ፡፡ አብዛኞቹ በፍርሃት
ገለል ገለል አሉ፡፡ የሚታፈሱ ነው የመሰላቸው፡፡
“ምን የተፈጠረ ነገር አለ? ምንድ ነው!” አንዱን ጐረምሣ ቢጤ አፋጠጠው፡፡
ለሱ አልታወቀውም እንጂ ልጁን እንደ ነፍሰ ገዳይ ኮሌታውን ጨምድዶ ይዞት ነበር፡፡
“ተጋደሉ በጥይት ወንፊት አደረጋት” አንገቱን ለማስለቀቅ እየሞከረ፡፡
“ማን ነው ማንን ወንፊት ያደረገው?” ተገላቢጦሹ ግራ ገባው።
“አትቀባጥር! ቀባጣሪ! ለወሬ ከመሽቀዳደምህ በፊት አጣራ!
ወሬኛ!” አለና አንዱ ጎረምሣ ልጁን ወደዚያ ገፍትሮ ወደ ሻምበል ብሩክ
ጠጋ አለ፡፡
“ጌታዬ እሷ ናት የመታችው፡፡ ደጋግማ ከተኮሰችበት በኋላ ለራሷ ጠጣች፡፡ በጣም የሚያሳዝን ነገር ነው፡፡ ይህን በዐይኔ በብረቱ ነው ያየሁት” አለና ምስክርነቱን ሰጠ፡፡
“ሞታለች?” ሻምበል ስውነቱ በብርክ እየተንቀጠቀጠ፡፡ ትሙት ትኑር አላውቅም፡፡ ከዚህ ወደ ሆስፒታል ሲወሰዱ ግን ሁለቱም በህይወት ነበሩ፡፡ የሚተርፉ ግን አይመስለኝም፡፡”
“የት ሆስፒታል ነው የተወሰዱት? ና እስቲ ግባ” ልጁን መኪና ውስጥ አስገባው፡፡ሁለቱም ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል መወሰዳቸው ተነገረውና፤ ተያይዘው ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በረሩ፡፡ሻምበል ብሩክ ነፍሱን አያውቅም፡፡ ሆስፒታል ደርሰው ወዲያና ወዲህ እየተራወጡ ስለ ሁኔታው ጠየቁ፡፡
አንዲት ነጭ ካፖርት የለበሰች ነርስ የሆነውን ቀስ ብላ አስረዳችው፡፡ ሁለቱም ጉዳተኞች በህይወት እንደሚገኙና በድንገተኛ ህክምና ክፍል እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ረጋ ብላ ገለፀችለት፡፡
“እውነትሽን ነው? አልሞተችም?” በሁለት እጆቹ ትከሻዋን ይዞ በጉጉት ጠየቃት፡፡
ይመኑኝ በተለይ እሷ ለህይወቷ የሚያሰጋ ጉዳት እንዳልደረሰባት ሀኪሞቹ ሲናገሩ በጆሮዬ ሰምቻለሁ፡፡” . ነፍሱን ትንሽ
መለስ አደረገችለት፡፡
“ምን እናድርግ አሁን ሲስተር? ደም የሚጠየቅ ከሆነ እባክሽን አጣሪልኝና
ደም ልስጥ፡፡ ሌላም የሚያስፈልገውን እርዳታ ሁሉ አሳውቂኝ፡፡ ሲስተር ትልቅ ባለውለታዬ ትሆኛለሽ፡፡ ተባበሪኝ” ተማፀናት፡፡
“ግድ የለዎትም አይረበሹ፡፡ የሚሆነውን ሁሉ በዶክተሮች ትዕዛዝ መሠረት እንፈጽማለን፡፡ እስከዚያው ይምጡ” አለችና ወስዳ አንድ ክፍል ውስጥ አረፍ እንዲል አደረገችው፡፡
ሁኔታው ስላሳዘናት ነው ትንሽ እረፍት እንዲወስድና፤ እራሱን እንዲያረጋጋ፤ የፈለገችው፡፡
ሻምበል ብሩክ አምላክ ነፍስ ገዳይ እንዳያደርገው በልቡ ፀሎት እያደረሰ፣ የሚሆነውን ሁሉ በሲስተር ማን አህሎች በኩል ለመሰማት በጉጉት መጠባበቁን ቀጠለ፡፡
“መኪናውን ይዘህ ሂድ” አለና ሾፌሩን ሸኘው፡፡ ለልጁ አምስት ብር አስጨብጦ ሁለቱንም ላክና፤ እሱ እዚያ ሆኖ ውጤቱን ይጠባበቅ ጀመር፡፡ አሁን ትንሽ ነፍሱ መለስ ስትልለት፤ አንድ ነገር ትዝ አለው፡፡
ለአዜብ እንዲደውልላት አደራ ብላው ነበር፡፡ የስልክ ቁጥሩን ከደብዳቤው ላይ አነበበና ለአዜብ ደወለላት፡፡ ዝም ብሎ በደፈናው ችግር መድረሱን ገልጾ፤
ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በአስቸኳይ እንድትመጣ ነገራት፡፡
አዜብ ይህንን ስትሰማ ክው ብላ ደንገጠች፡፡ አንዱአለም የሞተ መሰላት፡፡ ነፍሷን ሳታውቀው፤ ፀጉሯን እንኳን ሳታበጥር፤ እየከነፈች መጣች፡፡ ሻምበል ብሩክ በሩ ላይ ሆኖ
👍2
እየጠበቃት ነበር፡፡
“አንዱዓለም ሞተ?! ሞተ ሻምበል?!” ሰውነቷ ተረብሿል። እዚያ እሱቁ ድረስ ወስዳ እንደሻውን ያሳየችው እሷ ነች፡፡ ጦሱ የሷ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ሲሞት እሷ እንደገደለችው እየተርበተበተች ፤ ሻምበልን አፋጠጠችው፡፡
የተፈጠረው ተአምር ግን ከግምቷ ውጭ
ነበር፡፡ጭራሽ ይሆናል ብላ ልትገምተው የማትችለው አስደንጋጭ ሁኔታ! ሻምበል
እንዴት እንደሚገልጽላት ጨንቆት ዐይኖቹ ፈጠው ቀሩ...
“አንዱዓለም ምንም አልሆነም፡፡ አዜብ ሌላ ነገር ነው ትህትና እንደሻውን በጥይት ከመታችው በኋላ፣ እራሷን
“እናስ ከዛስ? እራሷን ምን?!!!...ጮኸች፡፡
“አራሷንም በጥይት ጐድታለች..
ኡይይ! ሞታለች በለኝ እንጂ ሻምበል! ጓደኛዬ ሞታለች በለኝ እንጂ!ትሁትዬ፣ ያልታደለችው ጓደኛዬ ሞታለች፡፡ ትሁት ሞታለች፣እንደሰው ሳይደላት እንደተቃጠለች ሞተች፡፡ እንዳለቀሰች ቀረች ጓደኛዬ ትሁትዬ? የት ነው ያለሽው? የኔ እመቤት! ጓዱ .... ጓደኛዬ እንደ እብደ ሆና እየጮኽች ወደ ግቢው ውስጥ ሩጫ ጀመረች፡፡
ሻምበል ተከትሏት ሮጠና፤ በግድ አጇን ይዞ አስቀራት፡፡ ወዴት ልትሄድ እንደነበረ እግዜር ይወቀው፡፡ እዚያ እመሬት ላይ ወድቃ በእንባ እየታጠበች አለቀሰች፡፡ የማትለው፤ የማትናገረው፤ ነገር የለም፡፡ ትህትና በህይወቷ አንድም ቀን ሳይደላት፤ እንደተሰቃየች፣እንደተቸገረች፣እንደተንከራተተች፤ መሞቷን፣ የሷ ደስታ ከሻምበል ጋር ያሳለፈችው አጭር ወቅት ብቻ መሆኑን፣ እየለፈለፈች አለቀሰች፡፡
ሻምበል አልቻለም፡፡አንጀቱ ከውስጥ ተንሰፈሰፈ፡፡ ድምፁን ውጦ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ፡፡ በአንድ በኩል እሱ እራሱ አልቃሽ፤ በአንድ በኩል ገላጋይ ሆነ፡፡
“እባክሽ ዝም በይ አዜብ፡፡ ደህና መሆኗን አረጋግጫለሁ፡፡
ለህይወቷ እንደማያሰጋት ተነግሮኛል። እባክሽ ዝም በይ” እንደዚያ ሆና በምሬት ስታለቅስ፤ በትህትና ላይ የደረሰው
የህይወት ፈተና፣ ስቃይዋ፣ እራሷን እስከማጥፋት የሚያደርስ መከራ
መሸክሟ፣ ንፁህነቷ፤ በሃሣብ ታየው፡፡
በተለይ እላዩ ላይ ጥምጥም ብላ፤ ስቅስቅ ብላ! ያለቀሰችው፣ እፊቱ ላይ ድቀን ቢልበት ... ሰውነቱ ተንቀጠቀጠ፡፡
አዜብ ትንሽ ቀዝቀዝ ስትል፤ ስለሁኔታው ከሀኪሞች አንደበት እንድትስማ! ወደ ሲስተር ማን አህሎሽ ዘንድ ይዟት ሄደ።
ሁሉንም አዜብ ትነግርሃለች ብላው ነበር፡፡ስለሁሉም ሁኔታ ዝርዝሩን ከአዜብ ሊሰማ፤ ደብዳቤውን ሰጣት፡፡ አዜብ ያንን ደብዳቤ እያለቀሰች አንብባ ከጨረሰች በኋላ፤ የሆነውን ሁሉ፤ አንድም ሳታስቀር እውነታውን ተረከችለት....
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
“አንዱዓለም ሞተ?! ሞተ ሻምበል?!” ሰውነቷ ተረብሿል። እዚያ እሱቁ ድረስ ወስዳ እንደሻውን ያሳየችው እሷ ነች፡፡ ጦሱ የሷ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ሲሞት እሷ እንደገደለችው እየተርበተበተች ፤ ሻምበልን አፋጠጠችው፡፡
የተፈጠረው ተአምር ግን ከግምቷ ውጭ
ነበር፡፡ጭራሽ ይሆናል ብላ ልትገምተው የማትችለው አስደንጋጭ ሁኔታ! ሻምበል
እንዴት እንደሚገልጽላት ጨንቆት ዐይኖቹ ፈጠው ቀሩ...
“አንዱዓለም ምንም አልሆነም፡፡ አዜብ ሌላ ነገር ነው ትህትና እንደሻውን በጥይት ከመታችው በኋላ፣ እራሷን
“እናስ ከዛስ? እራሷን ምን?!!!...ጮኸች፡፡
“አራሷንም በጥይት ጐድታለች..
ኡይይ! ሞታለች በለኝ እንጂ ሻምበል! ጓደኛዬ ሞታለች በለኝ እንጂ!ትሁትዬ፣ ያልታደለችው ጓደኛዬ ሞታለች፡፡ ትሁት ሞታለች፣እንደሰው ሳይደላት እንደተቃጠለች ሞተች፡፡ እንዳለቀሰች ቀረች ጓደኛዬ ትሁትዬ? የት ነው ያለሽው? የኔ እመቤት! ጓዱ .... ጓደኛዬ እንደ እብደ ሆና እየጮኽች ወደ ግቢው ውስጥ ሩጫ ጀመረች፡፡
ሻምበል ተከትሏት ሮጠና፤ በግድ አጇን ይዞ አስቀራት፡፡ ወዴት ልትሄድ እንደነበረ እግዜር ይወቀው፡፡ እዚያ እመሬት ላይ ወድቃ በእንባ እየታጠበች አለቀሰች፡፡ የማትለው፤ የማትናገረው፤ ነገር የለም፡፡ ትህትና በህይወቷ አንድም ቀን ሳይደላት፤ እንደተሰቃየች፣እንደተቸገረች፣እንደተንከራተተች፤ መሞቷን፣ የሷ ደስታ ከሻምበል ጋር ያሳለፈችው አጭር ወቅት ብቻ መሆኑን፣ እየለፈለፈች አለቀሰች፡፡
ሻምበል አልቻለም፡፡አንጀቱ ከውስጥ ተንሰፈሰፈ፡፡ ድምፁን ውጦ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ፡፡ በአንድ በኩል እሱ እራሱ አልቃሽ፤ በአንድ በኩል ገላጋይ ሆነ፡፡
“እባክሽ ዝም በይ አዜብ፡፡ ደህና መሆኗን አረጋግጫለሁ፡፡
ለህይወቷ እንደማያሰጋት ተነግሮኛል። እባክሽ ዝም በይ” እንደዚያ ሆና በምሬት ስታለቅስ፤ በትህትና ላይ የደረሰው
የህይወት ፈተና፣ ስቃይዋ፣ እራሷን እስከማጥፋት የሚያደርስ መከራ
መሸክሟ፣ ንፁህነቷ፤ በሃሣብ ታየው፡፡
በተለይ እላዩ ላይ ጥምጥም ብላ፤ ስቅስቅ ብላ! ያለቀሰችው፣ እፊቱ ላይ ድቀን ቢልበት ... ሰውነቱ ተንቀጠቀጠ፡፡
አዜብ ትንሽ ቀዝቀዝ ስትል፤ ስለሁኔታው ከሀኪሞች አንደበት እንድትስማ! ወደ ሲስተር ማን አህሎሽ ዘንድ ይዟት ሄደ።
ሁሉንም አዜብ ትነግርሃለች ብላው ነበር፡፡ስለሁሉም ሁኔታ ዝርዝሩን ከአዜብ ሊሰማ፤ ደብዳቤውን ሰጣት፡፡ አዜብ ያንን ደብዳቤ እያለቀሰች አንብባ ከጨረሰች በኋላ፤ የሆነውን ሁሉ፤ አንድም ሳታስቀር እውነታውን ተረከችለት....
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
....ለማንኛውም አሁን ከለማ ጋር ግንኙነታችን ተቋርጧል።
"በቃ?"
" አዎ " ከእንግዲህ በዚህ አይነት የምንቀጥል አይመስለኝም ። በእሱ የተነሣ ነው ፡ እንዲህ ስሜ የጠፋው ። ”
ሁለቱም ዝም አሉ። እስክንድር ለሁኔታው ያልተዘጋጀበት ሆኖ ነው ለአፋጣኝ ጥያቄም ሆና መልስ የተቸገረው።
ቤተልሄም ግን በዝምታው መርከብ ተሳፍራ ወደ ኋላዋ ከለማ ጋር የተጣሉበት ቀን ደርሳ ነበር።
የሁለተኛ ሴሚስተር ትምህርት ተጀምሮ ልማ ምንም ኮርስ እንደማያስተምራት ካረጋግጠች በኋላ ፥ ቤተልሔም ሸርተት ለማለት ትጀምራለች ። ጭራሹን ለአንድ ሳምንት ያህል ትሰወርበታለች።ለማ ልቡ ይጠረጥርና በዚያው ሳምንት ግቢ ውስጥ ፈልጎ ካገኛት በኋላ ፥ ቤቱ ድረስ እንድትመጣ ነብር ሆኖ ይቀጥራታል ።
"ምን ሆነሽ ነው እንዲህ የጠፋሽው!" እንደ ብራቅ ጮህባት።
"ስላልተመቸኝ ነው"
"ይህው ነው መልስሽ?" አላት በሽቆ።
ዐይኗን ሰብራ ዝም አለች ። አኳኋኑ አስፈራት ። ገላጋይ በሌለበት ባዶ ቤት ውስጥ የያዛት እንደሆን ማን ይደርስላታል ? ሽንቷ ወጠራት ።
"ምን መሰለህ ለማ" አለችው እንባ በተናነቀው ድምፅ ዬኒቨርስቲዉ ውስጥ ስሜን እያጠፉ ነው ። ከአንተ ጋር ባለኝ ግንኙነት ክፉኛ ታምቻለሁ ። ሰላም ይሉኝ የነበሩ ተማሪዎች ሁሉ ዘግተውኛል !
"እና ? ”
“ እና ለአንተም ስም ሆነ ለእኔ ይህን ግንኙነታችንን ብናቋርጠው ይሻላል ብዬ ነው። እኔ እዚያ ግቢ ውስጥ መኖር
እልቻልኩም ፡ ሰውነቴ አለቀ” አለችው ፡ ለቅሶ እየቃጣት
እንዲሁ ነች ። እስክንድርን ጠርታ ፥ “ ጓደኛዬ ሁን ” እንዳለችው መሆኑ ነው ። ብልጠቷ ስልት የለውም ። ይህ ስልት ያጣው ብልጠቷ ለማን አብከነከነው ።
“ ስሚ ! ” አላት ። መቀጠል አልቻለም ። ጉሮሮው ላይ የሆነ ነገር ተናነቀው ። ከወጣትነት ባለፈ ዕድሜው የእልህ ዕንባ እንዳያነባ ፈራ ። እናም ከምላሱ ይልቅ እጁን ማንቀሳቀስ መረጠ ። የራስጌ ኮመዲኖውን ከፍቶ አንድ ወረቀት አወጣና ሰጣት ።
ምንድነው ? አለችው ።
አንብቢው ! አላት ፡ ዐይኑን አፍጥጦ ።
በዚሁ ሳምንት ውስጥ ቢሮው ወስጥ በድብቅ ተጥሎ ያገኘው ወረቀት ነበር ። ቤተልሔም ተቀብው ማንበብ ጀመረች።
ጽሑፉ በቅጡ አልተቀነባበረም ። በግጥም ይጀምርና
ምሁር ሰማ ዘቀጠ ...
ኅሊናውን ለሴት ሽጠ ...
ካለ በኋላ ፥ በስድ ንባብ ይቀጥላል ። ቃላቱ ተስፋ መቁረጥን ያመለክታሉ ። በለማ ላይ የተደረደሩ ተራ ስድቦች ነበሩ ።
በመሐል ደግሞ
... ወሲብ አንጎል ሆኖ ሲያስመርቅ እያየሁ ፡ የእኔ ጥናት ከንቱ እንዲያው ተሠቃየሁ አወይ እኔ ፡ አወይ እኔ ! ሴት አለ መሆኔ !...” ይልና፡ ተመልሶ ስድቡን ይቀጥላል ።
አንብባ ጨርሳ ቀና ስትል፥ የምትናገረውን ለመስማት ዐይን ዐይኗን ተመለከታት ። ለእሷ ሲል የተጋፈጣቸው ችግሮች በውስጧ ኅዘን እንዲፈጥሩባት ነበር ሃሳቡ ። እንዲህ ዐይነት ነገሮችን ሥራዬ ብሎ ነው የሚነግራት ። አንዴም በመጀመሪያው ሴሚስተር አንድ ጓደኛው መቼም የቅርቤ ነው ብሎ ሊመክረው ፥ “ ለማ እዚህ ግቢ ውስጥ በአንዲት
ልጅ ምክንያት ስምህ እየተበከለ ነው ” ብሎ ሲጀምር' ለማ በሽቆ ፡ “ ስለዚህ ጉዳይ ምንም አታንሣብኝ ። ተፈጥሮን
ተመክሮ አይመልሰውም ! ማንም የፈለገውን ሊል ይችላል” ብሎ ዘግቶታል ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ መምህራንም
እየታዘቡት መሆናቸውን ሊነግረው ነበር ጓደኛዉ የፈለገው ነገር ግን ለማ የሚበገር ሰው አልሆነም።
በወቅቱ ይህንንም ለቤተልሔም አጯውቷታል ።በአንቺ የተነሳ ያየሁት አበሳ" አይነት መሆኑ ነው። ታዲያ ያኔ ቤተልሄም አዝና ከንፈሯን መጥጣለት
ነበር ።
"አበሻ ነገር መፈትፈት ልማዱ ነው ! አትጨነቅ ” በማለትም አበረታታዋለች ። አሁን ግን ግጥሙን አንብባ የዚያን ዐይነት መልስ አልሰጠችውም ፡፡ እንዲያውም ለአፍራሽ ሐሳቧ መንገድ የጠረገላት ነው የመሰላት......
እና ፥ ከዚህ ሁሉ ነገር በኋላ ወዴት ነው። ሸርተት የምትይው ? አላት አፍጥጦ።
“ እኔስ የፈራሁት ይህንኑ አይደል ? ” አለችና ጽሑፉ ክፉኛ እንደ ቆረቆራት ሁሉ ዐይኗን አሸች ። ዕንባው ደግሞ ራሱ ካልፈቀደ እንደ ፈለጉት አይመጣ ! ዐይኗን ምራቅ እንዳትቀባ ለማ አጠገቧ ቆሟል።
መጀመሪያ ለምን ነበር የቀረብሽው ? ” አላት እስክንድር።
" ፈራሁኛ ! ”
"ምን ? "
"ማትስ እንዳልወድቅ ። እኔ የቁጥር ዘር ጠላቴ ነው ።
ፍቅር ብቻ ሳይሆን እልህ ጭምር ነበር የያዘው ። አስተያየቱ አላማራትም ጡንቻው ላይ አባብጠው የተጋደሙት
ሥሮች አሰፈሯት ። ከተቀመጠችበት ቀስ ብላ ተነችና ወደ በሩ አምራች ።
የት ልትሔጂ ነው ? ” አለና ፥ አጠገቡ የነበረውን አምቦ ውሃ ጠርሙስ አንስቶ ግንባሯ ላይ አነጣጠረ።
“ውይ ለማ ! ” ብላ ጮሃ ጣውላው ላይ ቁጭ አለች ።
“ ሸርሙጣ ! ” አላት አጠገቧ ደርሶ ቁልቁል እየተመለከታት
የሚለማመጡና የተቆጡ ዐይኖች ሽቅብና ቁልቁል ተፋጠጡ ። ለማ ደፍሮ እጁን ሊያሳርፍባት አልቻለም ። አቅፎ
ለማባበልም ልቡ ያን ያህል አላላም ።
"ስሚ ፤ በሦስት ቀን ውስጥ አስበሽበት መልሱን ንገሪኝ። የሦስት ቀን ዕድሜ ሰጥቼሻለሁ ! ” አላት እንዳፈጠጠ ።
ቤተልሄም ከጣውላው ላይ ቶሎ አልተነሳችም” በድንጋጤ ከጭኗ ሥር ሽንት ጠብ ያለ ስለ መስላት እንዳይታይባት ፈራች ። ነገር ግን ሰውነቷን ዐልፎ ጣውላው ላይ
የደረሰ አልነበረም...
ያን ዕለት እንደ ምንም ከክፍሉ ከወጣች በኋላ መንገድ ላይ በጕዳዩ እሰበችበት ። የይህሆን ጨዋታ ነው ። የለማ ኮንትራት አልቋል ። አብራው ከቀጠለች ለሚቀጥሉት ዓላማዎቿ ዕንቅፋት ይሆንባታል ። ከአንድ ወንድ ጋር ብዙ መታየት ሴሎች የጥቅም መንገድን ወመዝጋት ነው ። ጥቅሙን የሚያሳድድ ሰው በአንድ ነገር ላይ መርጋት አይችልም ትርፉን ከኪሳራው እያሰላ በሚያዋጣው መንገድ መንቀሳቀስ አለበት ... እና ለማ እስኪረሳት ድረስ ከዐይኑ ለመሰወር ወሰነች። ከዚህ ውሳኔ በኋላ ስሟን ለማደስ በግቢው ውስጥ አብራው
የምትታይ ተማሪ ስታስብ ፥ እስክንድር በሐሳብዋ ብቅ አለ ። ብዙ ተማሪዎች ከዘጓት በኋላ እሱ ሳይለወጥ እንደ
ወትሮ ሰላም ይላት ስለ ነበር ነው የታሰባት......
እስክንድር በሆዱ ሣቀ። የግልጽ ሰው ሳይሆን የብልጥ አንበሳ ምስል ከፊቱ የቆመ መሰለው ለጥቅም የቆመች
አንበሳ ! ሣር ባየችበት ሁሉ የምታጎነብስ በግ ፤ ግን ደግሞ እንስሳ ለማዳ ነው ያበላውን ያጠጣውን ፥ የቀረበውን ቶሎ
ያፈቅራል ።
«ግን ታዲያ አብራችሁ ስትቆዩ ከለማ ጋር ፍቅር አልያዘሽም ? ” ሲል ጠየቃት ።
“ ኤጭ ! ” አለች በንቀት
"እሺ ፤ እሱስ ፍቅር ቢይዘው ኖሮ ? ”
“ እእይ እኔ አስቀድሜ ነግሬዋለሁ" አለች ግንባሯን አኮማትራ
"ምን ብለሽ ?
“ አሜሪካ የመሔድ ሐሳብ እንዳለኝ እጮኛዬ እየጠበቀኝ ነው።
ሣቁ እንዳያመልጠው እየሞከረ ፥ ዋና ይዘሽ በትርፍ እየተጫወትሽ ነዋ ! ” አላት
ፈገግ ብላ ዝም አለች ።
“የእኔም ጓደኝነትስ ምሽን እስካሳደርስሽ ድረስ ነዋ!”አላት ድንገት ግልፍ ብሎት ።
ወይኔ ! ካንተ ጋር እኮ እንዲሁ ጓደኝነት ነው ” አለችው ፥ ድንገተኛ ቁጣው አስደንግጧት ።
“ እንዲሁ ጓደኝነት ብሎ ነገር ምንድነው?” ሲል አሰበ። ሐሳቡ ከውስጥ ጥቀርሻ እየለበሰ ሲመጣ ተሰማው ። የአሁኗ
ቤተልሔም ሳትሆን ነገ የምትይዘው ቦታና የምትፈጽመው ተግባር ነው የታየው በዚህ ዐይነት ብላሽ ጥበብ ከዩኒቨርስቲ የምትረቅ ሴት ፥ በሥራ ዓለም ስትሠማራም መሰሎቿን ታፈራና ትመለምል እንደሆን እንጂ ያስተማራትን ሕዝብ
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
....ለማንኛውም አሁን ከለማ ጋር ግንኙነታችን ተቋርጧል።
"በቃ?"
" አዎ " ከእንግዲህ በዚህ አይነት የምንቀጥል አይመስለኝም ። በእሱ የተነሣ ነው ፡ እንዲህ ስሜ የጠፋው ። ”
ሁለቱም ዝም አሉ። እስክንድር ለሁኔታው ያልተዘጋጀበት ሆኖ ነው ለአፋጣኝ ጥያቄም ሆና መልስ የተቸገረው።
ቤተልሄም ግን በዝምታው መርከብ ተሳፍራ ወደ ኋላዋ ከለማ ጋር የተጣሉበት ቀን ደርሳ ነበር።
የሁለተኛ ሴሚስተር ትምህርት ተጀምሮ ልማ ምንም ኮርስ እንደማያስተምራት ካረጋግጠች በኋላ ፥ ቤተልሔም ሸርተት ለማለት ትጀምራለች ። ጭራሹን ለአንድ ሳምንት ያህል ትሰወርበታለች።ለማ ልቡ ይጠረጥርና በዚያው ሳምንት ግቢ ውስጥ ፈልጎ ካገኛት በኋላ ፥ ቤቱ ድረስ እንድትመጣ ነብር ሆኖ ይቀጥራታል ።
"ምን ሆነሽ ነው እንዲህ የጠፋሽው!" እንደ ብራቅ ጮህባት።
"ስላልተመቸኝ ነው"
"ይህው ነው መልስሽ?" አላት በሽቆ።
ዐይኗን ሰብራ ዝም አለች ። አኳኋኑ አስፈራት ። ገላጋይ በሌለበት ባዶ ቤት ውስጥ የያዛት እንደሆን ማን ይደርስላታል ? ሽንቷ ወጠራት ።
"ምን መሰለህ ለማ" አለችው እንባ በተናነቀው ድምፅ ዬኒቨርስቲዉ ውስጥ ስሜን እያጠፉ ነው ። ከአንተ ጋር ባለኝ ግንኙነት ክፉኛ ታምቻለሁ ። ሰላም ይሉኝ የነበሩ ተማሪዎች ሁሉ ዘግተውኛል !
"እና ? ”
“ እና ለአንተም ስም ሆነ ለእኔ ይህን ግንኙነታችንን ብናቋርጠው ይሻላል ብዬ ነው። እኔ እዚያ ግቢ ውስጥ መኖር
እልቻልኩም ፡ ሰውነቴ አለቀ” አለችው ፡ ለቅሶ እየቃጣት
እንዲሁ ነች ። እስክንድርን ጠርታ ፥ “ ጓደኛዬ ሁን ” እንዳለችው መሆኑ ነው ። ብልጠቷ ስልት የለውም ። ይህ ስልት ያጣው ብልጠቷ ለማን አብከነከነው ።
“ ስሚ ! ” አላት ። መቀጠል አልቻለም ። ጉሮሮው ላይ የሆነ ነገር ተናነቀው ። ከወጣትነት ባለፈ ዕድሜው የእልህ ዕንባ እንዳያነባ ፈራ ። እናም ከምላሱ ይልቅ እጁን ማንቀሳቀስ መረጠ ። የራስጌ ኮመዲኖውን ከፍቶ አንድ ወረቀት አወጣና ሰጣት ።
ምንድነው ? አለችው ።
አንብቢው ! አላት ፡ ዐይኑን አፍጥጦ ።
በዚሁ ሳምንት ውስጥ ቢሮው ወስጥ በድብቅ ተጥሎ ያገኘው ወረቀት ነበር ። ቤተልሔም ተቀብው ማንበብ ጀመረች።
ጽሑፉ በቅጡ አልተቀነባበረም ። በግጥም ይጀምርና
ምሁር ሰማ ዘቀጠ ...
ኅሊናውን ለሴት ሽጠ ...
ካለ በኋላ ፥ በስድ ንባብ ይቀጥላል ። ቃላቱ ተስፋ መቁረጥን ያመለክታሉ ። በለማ ላይ የተደረደሩ ተራ ስድቦች ነበሩ ።
በመሐል ደግሞ
... ወሲብ አንጎል ሆኖ ሲያስመርቅ እያየሁ ፡ የእኔ ጥናት ከንቱ እንዲያው ተሠቃየሁ አወይ እኔ ፡ አወይ እኔ ! ሴት አለ መሆኔ !...” ይልና፡ ተመልሶ ስድቡን ይቀጥላል ።
አንብባ ጨርሳ ቀና ስትል፥ የምትናገረውን ለመስማት ዐይን ዐይኗን ተመለከታት ። ለእሷ ሲል የተጋፈጣቸው ችግሮች በውስጧ ኅዘን እንዲፈጥሩባት ነበር ሃሳቡ ። እንዲህ ዐይነት ነገሮችን ሥራዬ ብሎ ነው የሚነግራት ። አንዴም በመጀመሪያው ሴሚስተር አንድ ጓደኛው መቼም የቅርቤ ነው ብሎ ሊመክረው ፥ “ ለማ እዚህ ግቢ ውስጥ በአንዲት
ልጅ ምክንያት ስምህ እየተበከለ ነው ” ብሎ ሲጀምር' ለማ በሽቆ ፡ “ ስለዚህ ጉዳይ ምንም አታንሣብኝ ። ተፈጥሮን
ተመክሮ አይመልሰውም ! ማንም የፈለገውን ሊል ይችላል” ብሎ ዘግቶታል ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ መምህራንም
እየታዘቡት መሆናቸውን ሊነግረው ነበር ጓደኛዉ የፈለገው ነገር ግን ለማ የሚበገር ሰው አልሆነም።
በወቅቱ ይህንንም ለቤተልሔም አጯውቷታል ።በአንቺ የተነሳ ያየሁት አበሳ" አይነት መሆኑ ነው። ታዲያ ያኔ ቤተልሄም አዝና ከንፈሯን መጥጣለት
ነበር ።
"አበሻ ነገር መፈትፈት ልማዱ ነው ! አትጨነቅ ” በማለትም አበረታታዋለች ። አሁን ግን ግጥሙን አንብባ የዚያን ዐይነት መልስ አልሰጠችውም ፡፡ እንዲያውም ለአፍራሽ ሐሳቧ መንገድ የጠረገላት ነው የመሰላት......
እና ፥ ከዚህ ሁሉ ነገር በኋላ ወዴት ነው። ሸርተት የምትይው ? አላት አፍጥጦ።
“ እኔስ የፈራሁት ይህንኑ አይደል ? ” አለችና ጽሑፉ ክፉኛ እንደ ቆረቆራት ሁሉ ዐይኗን አሸች ። ዕንባው ደግሞ ራሱ ካልፈቀደ እንደ ፈለጉት አይመጣ ! ዐይኗን ምራቅ እንዳትቀባ ለማ አጠገቧ ቆሟል።
መጀመሪያ ለምን ነበር የቀረብሽው ? ” አላት እስክንድር።
" ፈራሁኛ ! ”
"ምን ? "
"ማትስ እንዳልወድቅ ። እኔ የቁጥር ዘር ጠላቴ ነው ።
ፍቅር ብቻ ሳይሆን እልህ ጭምር ነበር የያዘው ። አስተያየቱ አላማራትም ጡንቻው ላይ አባብጠው የተጋደሙት
ሥሮች አሰፈሯት ። ከተቀመጠችበት ቀስ ብላ ተነችና ወደ በሩ አምራች ።
የት ልትሔጂ ነው ? ” አለና ፥ አጠገቡ የነበረውን አምቦ ውሃ ጠርሙስ አንስቶ ግንባሯ ላይ አነጣጠረ።
“ውይ ለማ ! ” ብላ ጮሃ ጣውላው ላይ ቁጭ አለች ።
“ ሸርሙጣ ! ” አላት አጠገቧ ደርሶ ቁልቁል እየተመለከታት
የሚለማመጡና የተቆጡ ዐይኖች ሽቅብና ቁልቁል ተፋጠጡ ። ለማ ደፍሮ እጁን ሊያሳርፍባት አልቻለም ። አቅፎ
ለማባበልም ልቡ ያን ያህል አላላም ።
"ስሚ ፤ በሦስት ቀን ውስጥ አስበሽበት መልሱን ንገሪኝ። የሦስት ቀን ዕድሜ ሰጥቼሻለሁ ! ” አላት እንዳፈጠጠ ።
ቤተልሄም ከጣውላው ላይ ቶሎ አልተነሳችም” በድንጋጤ ከጭኗ ሥር ሽንት ጠብ ያለ ስለ መስላት እንዳይታይባት ፈራች ። ነገር ግን ሰውነቷን ዐልፎ ጣውላው ላይ
የደረሰ አልነበረም...
ያን ዕለት እንደ ምንም ከክፍሉ ከወጣች በኋላ መንገድ ላይ በጕዳዩ እሰበችበት ። የይህሆን ጨዋታ ነው ። የለማ ኮንትራት አልቋል ። አብራው ከቀጠለች ለሚቀጥሉት ዓላማዎቿ ዕንቅፋት ይሆንባታል ። ከአንድ ወንድ ጋር ብዙ መታየት ሴሎች የጥቅም መንገድን ወመዝጋት ነው ። ጥቅሙን የሚያሳድድ ሰው በአንድ ነገር ላይ መርጋት አይችልም ትርፉን ከኪሳራው እያሰላ በሚያዋጣው መንገድ መንቀሳቀስ አለበት ... እና ለማ እስኪረሳት ድረስ ከዐይኑ ለመሰወር ወሰነች። ከዚህ ውሳኔ በኋላ ስሟን ለማደስ በግቢው ውስጥ አብራው
የምትታይ ተማሪ ስታስብ ፥ እስክንድር በሐሳብዋ ብቅ አለ ። ብዙ ተማሪዎች ከዘጓት በኋላ እሱ ሳይለወጥ እንደ
ወትሮ ሰላም ይላት ስለ ነበር ነው የታሰባት......
እስክንድር በሆዱ ሣቀ። የግልጽ ሰው ሳይሆን የብልጥ አንበሳ ምስል ከፊቱ የቆመ መሰለው ለጥቅም የቆመች
አንበሳ ! ሣር ባየችበት ሁሉ የምታጎነብስ በግ ፤ ግን ደግሞ እንስሳ ለማዳ ነው ያበላውን ያጠጣውን ፥ የቀረበውን ቶሎ
ያፈቅራል ።
«ግን ታዲያ አብራችሁ ስትቆዩ ከለማ ጋር ፍቅር አልያዘሽም ? ” ሲል ጠየቃት ።
“ ኤጭ ! ” አለች በንቀት
"እሺ ፤ እሱስ ፍቅር ቢይዘው ኖሮ ? ”
“ እእይ እኔ አስቀድሜ ነግሬዋለሁ" አለች ግንባሯን አኮማትራ
"ምን ብለሽ ?
“ አሜሪካ የመሔድ ሐሳብ እንዳለኝ እጮኛዬ እየጠበቀኝ ነው።
ሣቁ እንዳያመልጠው እየሞከረ ፥ ዋና ይዘሽ በትርፍ እየተጫወትሽ ነዋ ! ” አላት
ፈገግ ብላ ዝም አለች ።
“የእኔም ጓደኝነትስ ምሽን እስካሳደርስሽ ድረስ ነዋ!”አላት ድንገት ግልፍ ብሎት ።
ወይኔ ! ካንተ ጋር እኮ እንዲሁ ጓደኝነት ነው ” አለችው ፥ ድንገተኛ ቁጣው አስደንግጧት ።
“ እንዲሁ ጓደኝነት ብሎ ነገር ምንድነው?” ሲል አሰበ። ሐሳቡ ከውስጥ ጥቀርሻ እየለበሰ ሲመጣ ተሰማው ። የአሁኗ
ቤተልሔም ሳትሆን ነገ የምትይዘው ቦታና የምትፈጽመው ተግባር ነው የታየው በዚህ ዐይነት ብላሽ ጥበብ ከዩኒቨርስቲ የምትረቅ ሴት ፥ በሥራ ዓለም ስትሠማራም መሰሎቿን ታፈራና ትመለምል እንደሆን እንጂ ያስተማራትን ሕዝብ
👍4
ምን ያህል ትረዳለች ? ”
አንቺና መሰሎችሽ ተመርቃችሁ በምትይዙት ቦታም የኅብረተሰቡ በሽታ ነው የምትሆኑት ! ሊላት ፈለገ ። ግን
በምላሱ እንዲህ አምርሮ ሊያስቀይማት አልደፈረም ። “ ይልቅስ ለምን ቀርቤያት ከጥፋቷ እንድትማር አላደርጋትም ?
ሴት ልጅ ውበቷንና ገላዋን ለፍቅር እንጂ ለጥቅም መሸጥ የለባትም ፡ ካለዚያ ውሎ ሲያድር እንደ ዕቃ መቆጠር ይመጣል ብዬ ለምን አልመክራትም ? እንዲህ ዐይነቱ ከንቱ ብልጠት ከቤተልሔም ጋር አብሯት አልተወለደ ፤ ከኖረችበት አካባቢ የቀሠመችው በሽታ ነው እንጂ " እኔ ከማግለል ማስተማሩ አይሻልም ? ” የሚል የኅሊና ሙግት ገጠመው ።
ከሐሳቡ በስተጀርባ የችኮላ ስሜት ወጥሮት ነበር ።ወዴት ለመሔድ እንደ ቸኮለ አልገባውም። የሚሔድበትም
ጉዳይ አልነበረውም ።ከትዕግሥት ጋር የተያያዘ ስሜት ነበር የወጠረው ። እሷ ለአል ደብዳቤ ልትጽፍለት መሆኑን
ለቅርቡ ሰው አጫውቶ ተንፍሶ እንዲወጣለት ይፈልጋል ግን ለማን ? ለአሥራት ? ለቢልልኝ? ለዮናታን ?...
"ምነው ዝም አልክ ? ” አለችው ቤተልሄም ዝምታው አስከፍቶአት።
"እእይ ፤ እንዲሁ ነው" አለና "ግድየለሽም
ግኝኙነታችን እንደ ጥንቱ ቢቀጥል ይሻላል ” አላት እያመነታ።
አኩርፋ ለመሄድ ተነሣች።
“ እፎይ ትሒድልኝ ”አለ እስንድር በልቡ...
💥ይቀጥላል💥
አንቺና መሰሎችሽ ተመርቃችሁ በምትይዙት ቦታም የኅብረተሰቡ በሽታ ነው የምትሆኑት ! ሊላት ፈለገ ። ግን
በምላሱ እንዲህ አምርሮ ሊያስቀይማት አልደፈረም ። “ ይልቅስ ለምን ቀርቤያት ከጥፋቷ እንድትማር አላደርጋትም ?
ሴት ልጅ ውበቷንና ገላዋን ለፍቅር እንጂ ለጥቅም መሸጥ የለባትም ፡ ካለዚያ ውሎ ሲያድር እንደ ዕቃ መቆጠር ይመጣል ብዬ ለምን አልመክራትም ? እንዲህ ዐይነቱ ከንቱ ብልጠት ከቤተልሔም ጋር አብሯት አልተወለደ ፤ ከኖረችበት አካባቢ የቀሠመችው በሽታ ነው እንጂ " እኔ ከማግለል ማስተማሩ አይሻልም ? ” የሚል የኅሊና ሙግት ገጠመው ።
ከሐሳቡ በስተጀርባ የችኮላ ስሜት ወጥሮት ነበር ።ወዴት ለመሔድ እንደ ቸኮለ አልገባውም። የሚሔድበትም
ጉዳይ አልነበረውም ።ከትዕግሥት ጋር የተያያዘ ስሜት ነበር የወጠረው ። እሷ ለአል ደብዳቤ ልትጽፍለት መሆኑን
ለቅርቡ ሰው አጫውቶ ተንፍሶ እንዲወጣለት ይፈልጋል ግን ለማን ? ለአሥራት ? ለቢልልኝ? ለዮናታን ?...
"ምነው ዝም አልክ ? ” አለችው ቤተልሄም ዝምታው አስከፍቶአት።
"እእይ ፤ እንዲሁ ነው" አለና "ግድየለሽም
ግኝኙነታችን እንደ ጥንቱ ቢቀጥል ይሻላል ” አላት እያመነታ።
አኩርፋ ለመሄድ ተነሣች።
“ እፎይ ትሒድልኝ ”አለ እስንድር በልቡ...
💥ይቀጥላል💥
👍1
እሠይ ስሞ አገኘኹ፤
በሰው አፍ ተገኘኹ፡፡
"እሱ"... መባል ያዘ፤ መከረኛው ስሜ፤
መነከስ ጀመርኩኝ ፤ ጨረስኩኝ ተስሜ፡፡
ሰየሙልሽ፤
መዘኑልሽ፤
ሰፈሩልሽ፤
መተሩልሽ፤
መከሩልሽ፤
መከሩብሽ፤
"ከሴት ሴት አይቶ ፣ አይመኝም ደሞ
ሌላ ሴት ያስባል ፤ካንቺ ጋር ተጋድሞ።"
ይሉሻል!
“ከአንድ ግጥሙ ፣ እንኳን አበልጦ አያይሽም፤
ካልመሽበት በቀር ፣ ካንቺ አያመሽሞ።"
ይሉሻል!
የኔ ዓለሞ ሐቅ ነው!
ትልቅ ውሸት ሳይኮን ፣ ቅንጣት ውሸት የለው።
የኔ ዓላሞ ሐቅ ነው!
አሙልሽ አይደል ፣ የኔን ብሽቀት ላንቺ ፣ እያደማመቁ?
የሚያመትን እኔን...
አንቺ እንደፈጠርሽው፣መች እነ'ሱ አወቁ።?
🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘
በሰው አፍ ተገኘኹ፡፡
"እሱ"... መባል ያዘ፤ መከረኛው ስሜ፤
መነከስ ጀመርኩኝ ፤ ጨረስኩኝ ተስሜ፡፡
ሰየሙልሽ፤
መዘኑልሽ፤
ሰፈሩልሽ፤
መተሩልሽ፤
መከሩልሽ፤
መከሩብሽ፤
"ከሴት ሴት አይቶ ፣ አይመኝም ደሞ
ሌላ ሴት ያስባል ፤ካንቺ ጋር ተጋድሞ።"
ይሉሻል!
“ከአንድ ግጥሙ ፣ እንኳን አበልጦ አያይሽም፤
ካልመሽበት በቀር ፣ ካንቺ አያመሽሞ።"
ይሉሻል!
የኔ ዓለሞ ሐቅ ነው!
ትልቅ ውሸት ሳይኮን ፣ ቅንጣት ውሸት የለው።
የኔ ዓላሞ ሐቅ ነው!
አሙልሽ አይደል ፣ የኔን ብሽቀት ላንቺ ፣ እያደማመቁ?
የሚያመትን እኔን...
አንቺ እንደፈጠርሽው፣መች እነ'ሱ አወቁ።?
🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
በድንገት የተከሰተው አደጋ ክፉኛ ስላስደነገጠው ሻምበል ብሩክ ቀን እረፍት፤ ሌት እንቅልፍ፤ የሚባል ነገር አጥቶ እንደዚሁ በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ከረመ፡፡ ለዚሁ ጉዳይ ሲልም ከመስሪያ ቤቱ የአስራ አምስት ቀን ፈቃድ ወሰደ፡፡ በዚህ ፈቃድ በወሰደበት ጊዜው
ውስጥ ደግሞ ብዙ መሯሯጥ ይጠበቅበታል፡፡መጀመሪያ ሆስፒታል የተኛች እናቷን ማረጋጋት አለበት :: ከዚያም ለወንድሟ በቂና አሳማኝ ምክንያት መስጠት ይጠበቅበታል ይህንን ሁሉ ሲያደርግ በሀሳብ የምትረዳውና ! አብራው የምትሯሯጠው! አዜብ ብቻ ነች፡፡ አዜብ ስለደረሰው አደጋ የትህትና አክስት እንዲያውቁት ፈልጋ ነበር፡፡
"አይሆንም ትርፉ ማስደንገጥ ብቻ ነው የሚሆነው፡፡ እነሱ ካወቁ ወሬው መዛመቱና፤ እናትዋ ጆሮ መድረሱ የማይቀር ስለሚሆን፤ በሚስጥር ቢያዝ ይሻላል” በማለት የተከራከረው ሻምበል
ነው፡፡ሻምበል ለእናቷ የሚሰጠው ምክንያት አሳማኝ እንዲሆን ሀሳብ
ሲያወጣና፧ ሲያወርድ፤ አዜብም እንደዚሁ ያሳምናታል ብላ ያሰበችውን ምክንያት ስትደረድር፤ ቆዩና ሁለቱም ይሆናል ባሉት ሃሳብ ላይ በጋራ ከተስማሙ በኋላ፤ ይህንኑ ሊያስረዳ ወደ የካቲት አስራ
ሁለት ሆስፒታል አቀና፡፡ ትህትና ከእናትዋ ጋር በአይነ ስጋ ከተገናኙ ሶስት ቀን ሆኗቸዋል፡፡ አንዱአለምም ድምጹ ከጠፋ ሳምንት አልፎታል፡፡በነገሩ እናት ግራ ተጋብታለች፡፡
"ልጆቼን ምን ነካብኝ?" በሚል ጭንቀት ተውጣለች፡፡ትናንትና ሆስፒታል መጥታ ያስተዳደረቻት ሰራተኛዋ ነበረች፡፡ ትህትና ከቤት ያለማደሯን ብቻ ነው የነገረቻት፡፡ በሽታዋን ማዳመጡን ትታ ልጆችዋን
እያብሰለሰለች፤ በሀሳብ እንደተዋጠች ነበር ሻምበል ብሩክ የደረሰው፡፡ብሩክን ስታየው በደስታ ልቧ ቀጥ አለች ::
"ትህትናዬስ ብሩኬ?" ከኪሱ አውጥቶ ይሰጣት ይመስል በጉጉት አይን አይኑን እያየች ጠየቀቸው፡፡ ሻምበል ብሩክ እንደማፈር ብሎ ሳቅ አለና፤ ተቅለሰለሰ፡፡ ለዘዴው...
“ምነው ብሩኬ በደህና ነው?" ከሁኔታው የከፋ ችግር እንደሌለ ተረድታለች፡፡
“ምንም ችግር የለም እማማ፡፡ ምን የኛ የወጣቶች ነገር...
የሚያሰጋ ነገር ያለመኖሩን ከሁኔታው ብትገነዘብም ምክንያቱን ለማወቅ
ቸኮለች፡፡
"ምንድነው እሱ ታዲያ?
ትህትና ምንም እንኳ እጮኛዬ ብትሆንም፤ ከትዳር በፊት እርግዝና ማለት፤ ትንሽ ያልተለመደ ስለሆነ... አንጠልጥሎ ተወው። ነገሩ ገባት
ከዚያ በላይ ልታስጨንቀው አልፈለገችም እሱ ግን ቀጠለ "ከጋብቻ በፊት ልጅ መውለድ የቤተሰብን ክብር መንካት ነው የሚል እምነት አላት፡፡ ተመካከርንና ማህጸኗ እንዲጠረግላት አደረግን፡፡ አሁን
ራስ ደስታ ሆስፒታል ትንሸ እረፍት ትውለድ ስላሉኝ አስተኝቻታለሁ።"አለና አጭር ድራማውን አጠናቀቀ፡፡ እናት የልጇን አቋም በእርግጥ ታውቀዋለች፡፡
አባቷ ያሳደጋትም በዚያ እምነት ጸንታ
እንድትኖር ነውና፤ በወሰደችው እርምጃ የተቃወሞ ድምጽ አላሰማችም፡፡
ነገሩን ውስጥ ውስጡን ስታብላላ ቆየችና......
“ሻምበል አደራህን! ትሁቴ ህጻን ልጅ ናት።እንደታላቅ ወንድም ተንከባከባት፡፡ እሷ ምኑንም የማታውቅ አንድ ፍሬ
ልጅ ናት፡፡ ለመጠንቀቁም ቢሆን አንተ ትሻላለህ፡፡ እሷ ምኑን ታውቀዋለች ብለህ
ነው?" የአሁኑ ስህተት እንዳይደገምና፤ በሌላ ጊዜ ተጨማሪ ጉዳት
እንዳይደርስባት፤ ሻምበል ሃላፊነቱን እንዲወጣ በማሳሰብ፤ አደራዋን
አጠበቀች፡፡ እሱም ትህትና ከሆስፒታል እንደወጣች ይዟት እንደሚመጣ
ቃል ገባላት፡፡ በመጠኑም ቢሆን ልቧ ትንሽ እረፍት አገኘ፡፡
“የአንዱአለሜ ወሬስ ? ምነው ጭልጥ ብሎ ጠፋ?" አከታትላ ጠየቀችው፡፡
“እኔ ራሴ ካገኘሁት ሳምንት ሆኖኛል እማማ፡፡ ለፈተናው ዝግጅት ሸፍቷል፡፡ ዘንድሮ አንደኛ ካልወጣሁ ሰው አይደለሁም ሲል የፎከረውን ለመፈፀም ቆርጦ መነሳቱን ትህትና ነግራኛለች። ምንም አያስቡ፤ ፈተናውን እንደጨረሰ እንዲመጣ እነግረዋለሁ።” ምክንያቱ
ብዙ ባይዋጥላትም የሻምበልን የማፅናኛ ቃል ከማዳመጥ በስተቀር አማራጭ አልነበራትም፡፡ዝም አለች፡፡ ከዚያም ሻምበል በግማሽ ልቡ ሆኖ፤ የሆነ ያልሆነውን፤ ሲያወራት ከቆየ በኋላ፤ ተሰናብቷት ወደ ትህትና ሩጫውን ቀጠለ....
ትህትና የቀዶ ህክምና ከተደረገላት በኋላ በአንደኛ ማእረግ እንድትተኛ ያደረገው ሻምበል ብሩክ ነው፡፡ ሻምበል አስፈላጊውን ክፍያ በመፈጸም ንጽህናው በተጠበቀና፤ ተጨማሪ በሽተኛ በሌለበት
አንደኛ ማእረግ ውስጥ እንድትተኛ የፈለገበት ዋናው ምክንያት፤
በሚተኙ በሽተኞች ስቃይ ተጨማሪ የአእምሮ መረበሽ ሊደርስባት ይችላል በሚል ፍራቻ ነው፡፡
ለቀዶ ጥገናው የተወጋችው ማደንዘዣ ስራውን በማጠናቀቁ ለአስቸኳይ ህክምናው በተሰጣት በሀያ አራት ሰአት ውስጥ ከሰመመናዊ እንቅልፉ ነቃችና አይኗን ገለጥ አደረገችው፡፡ ጣሪያውን ተመለከተች፡፡ ዙሪያዋን ቃኘች
የት እንዳለች፤ ምን እንደሆነች፤ በፍጹም
አታውቀውም፡፡ የተወጋችው የእንቅልፍ
መርፌ ፤ በጥይት የቆሰለው ሰውነቷና
እንደ ጉድ የፈሰሰው ደሟ መላ
አካሏን ድቅቅ አድርጐታል፡፡ከግራ ጆሮዋ ጀምሮ ፊቷ በአጠቃላይ በፋሻ ተሸፍኗል፡፡በክንዷ ላይ የተሰካውን ግሉኮስ ተመለከተችው፡፡ ጠብ ጠብ... እያለ
ይወርዳል። እንደገና አይኗን ጨፈነች፡፡ትንሽ ቆየችና መልሳ ገለጠችው::
እንደገና በሀሳብ ባህር ውስጥ ገባች፡፡ ምን ነበር የሆነው ? የት ነው ያለችው? እዚህ ለምን መጣች? እሷ ማን ነች? ቆይ .. ቆ ይ.. ምን ነበር የሆነው ? የሆነ
ነገር ብዥ ፧ ብዥ አለባት እንዴ ?..
መርካቶ ውስጥ እንደሻውን... ከዚያ በኋላ እራሷን... እንዴ?
ምንድነው ነገሩ? እሷ ሞታለች አይደለም እንዴ? በሰማይ ቤት ነው ወይንስ በምድር ላይ ያለችው? በዚያች በተሰናበተቻት ምድር ላይ? በፍጹም ሊሆን አይችልም! እንቆቅልሹም ሊገባት አልቻለም፡፡ ከዚያም ፊት ለፊትዋ የተቀመጡትን ሰዎች ትኩር ብላ ተመለከተቻቸው፡፡
ብዥ ፤ ብ ዥ ፤አሉባት አላወቀቻቸውም :: እነሱ በሀዘን ተውጠው አይን አይኗን ይመለከቷታል፡፡ እንደገና ትኩር ብላ ከመታሸግ በተረፈው በቀኝ አይኗ አየቻቸው፡፡ አሁንም አላወቀቻቸውም፡፡ እንቅስቃሴ የላትም፡፡እዚያ ከፊት ለፊቷ ሆነው በሀዘን ኩርምት ጭብጥ ብለው የተቀመጡትን ሰዎች በድጋሜ በጥንቃቄ ተመለከተቻቸው፡፡ የሆነ ምስል መጣላት፡፡
የምታውቀው ምስል በርቀት የምታውቀው ምስል.. አዎን
ታውቃቸዋለች እንጂ !! እንዴ..? በሚገባ ታውቃቸዋለች :: ቀስ ብላ በለሆሳስ ተጣራች "ብ..ሩ. ኬ..... አ . ዜ. ቢ . ና
እህህህ....." በዚህ ጊዜ አዜብ ቀስ ብላ ተነሳችና ሄዳ አጠገቧ ቆመች፡፡ ብሩክም አዜብን ተከትሎ ወደ አልጋው ተጠጋ፡፡ሻምበል እንደዚያ ሆና ሊያያት አልቻለም :: እንባው አመለጠውና ቀስ ብሎ ጉንጮቹን
እያቋረጠ ፈሰሰ፡፡
“እ ማ ዬ...ደ ህ...ና. ነች? ..አ.ን.ዱ.ዬስ..?"
"ሁለቱም በጣም ደህና ናቸው፡፡ ስለ እነሱ ምንም አታስቢ፡፡ እኛ አለን፡፡ አሁን ዋናው ማሰብ ያለብሽ ስለራስሽ ጤንነት ብቻ ነው እሺ?” አዜብ ነበረች፡፡
“እ..ሺ በደከመ ድምጽ፡፡
“ትሁት አዜብ የምትልሽን ስሚያት፡፡ስለ እማማ ምንም የሚያስጨንቅሽ ነገር የለም፡፡እሳቸው አንቺ ስለጠፋሽባቸው ነው ትንሽ ያሰቡት እንጂ በጣም ደህና ናቸው፡፡ ቶሎ ድነሽ ሄደሽ እንዲያዩሽ
በሃሳብና በጭንቀት ራስሽን መጉዳት የለብሽም፡፡ እሺ? አንዱ አለምም ድኗል ማለት ይቻላል፡፡ሰሞኑን መጥቶ ይጠይቅሻል እሺ?” ጉንጮቿን
እየዳበሰ፡፡
እሺ” አለች በድጋሜ፡፡ በዚያው ድክምክም ባለ ድምጿ። አሉኝ የምትላቸውና የምትተማመንባቸው ሁለቱ ጓደኞቿ፤ ደራሾቿ ፤ በዚህ በክፉ ቀን እንኳ ከጐኗ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
በድንገት የተከሰተው አደጋ ክፉኛ ስላስደነገጠው ሻምበል ብሩክ ቀን እረፍት፤ ሌት እንቅልፍ፤ የሚባል ነገር አጥቶ እንደዚሁ በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ከረመ፡፡ ለዚሁ ጉዳይ ሲልም ከመስሪያ ቤቱ የአስራ አምስት ቀን ፈቃድ ወሰደ፡፡ በዚህ ፈቃድ በወሰደበት ጊዜው
ውስጥ ደግሞ ብዙ መሯሯጥ ይጠበቅበታል፡፡መጀመሪያ ሆስፒታል የተኛች እናቷን ማረጋጋት አለበት :: ከዚያም ለወንድሟ በቂና አሳማኝ ምክንያት መስጠት ይጠበቅበታል ይህንን ሁሉ ሲያደርግ በሀሳብ የምትረዳውና ! አብራው የምትሯሯጠው! አዜብ ብቻ ነች፡፡ አዜብ ስለደረሰው አደጋ የትህትና አክስት እንዲያውቁት ፈልጋ ነበር፡፡
"አይሆንም ትርፉ ማስደንገጥ ብቻ ነው የሚሆነው፡፡ እነሱ ካወቁ ወሬው መዛመቱና፤ እናትዋ ጆሮ መድረሱ የማይቀር ስለሚሆን፤ በሚስጥር ቢያዝ ይሻላል” በማለት የተከራከረው ሻምበል
ነው፡፡ሻምበል ለእናቷ የሚሰጠው ምክንያት አሳማኝ እንዲሆን ሀሳብ
ሲያወጣና፧ ሲያወርድ፤ አዜብም እንደዚሁ ያሳምናታል ብላ ያሰበችውን ምክንያት ስትደረድር፤ ቆዩና ሁለቱም ይሆናል ባሉት ሃሳብ ላይ በጋራ ከተስማሙ በኋላ፤ ይህንኑ ሊያስረዳ ወደ የካቲት አስራ
ሁለት ሆስፒታል አቀና፡፡ ትህትና ከእናትዋ ጋር በአይነ ስጋ ከተገናኙ ሶስት ቀን ሆኗቸዋል፡፡ አንዱአለምም ድምጹ ከጠፋ ሳምንት አልፎታል፡፡በነገሩ እናት ግራ ተጋብታለች፡፡
"ልጆቼን ምን ነካብኝ?" በሚል ጭንቀት ተውጣለች፡፡ትናንትና ሆስፒታል መጥታ ያስተዳደረቻት ሰራተኛዋ ነበረች፡፡ ትህትና ከቤት ያለማደሯን ብቻ ነው የነገረቻት፡፡ በሽታዋን ማዳመጡን ትታ ልጆችዋን
እያብሰለሰለች፤ በሀሳብ እንደተዋጠች ነበር ሻምበል ብሩክ የደረሰው፡፡ብሩክን ስታየው በደስታ ልቧ ቀጥ አለች ::
"ትህትናዬስ ብሩኬ?" ከኪሱ አውጥቶ ይሰጣት ይመስል በጉጉት አይን አይኑን እያየች ጠየቀቸው፡፡ ሻምበል ብሩክ እንደማፈር ብሎ ሳቅ አለና፤ ተቅለሰለሰ፡፡ ለዘዴው...
“ምነው ብሩኬ በደህና ነው?" ከሁኔታው የከፋ ችግር እንደሌለ ተረድታለች፡፡
“ምንም ችግር የለም እማማ፡፡ ምን የኛ የወጣቶች ነገር...
የሚያሰጋ ነገር ያለመኖሩን ከሁኔታው ብትገነዘብም ምክንያቱን ለማወቅ
ቸኮለች፡፡
"ምንድነው እሱ ታዲያ?
ትህትና ምንም እንኳ እጮኛዬ ብትሆንም፤ ከትዳር በፊት እርግዝና ማለት፤ ትንሽ ያልተለመደ ስለሆነ... አንጠልጥሎ ተወው። ነገሩ ገባት
ከዚያ በላይ ልታስጨንቀው አልፈለገችም እሱ ግን ቀጠለ "ከጋብቻ በፊት ልጅ መውለድ የቤተሰብን ክብር መንካት ነው የሚል እምነት አላት፡፡ ተመካከርንና ማህጸኗ እንዲጠረግላት አደረግን፡፡ አሁን
ራስ ደስታ ሆስፒታል ትንሸ እረፍት ትውለድ ስላሉኝ አስተኝቻታለሁ።"አለና አጭር ድራማውን አጠናቀቀ፡፡ እናት የልጇን አቋም በእርግጥ ታውቀዋለች፡፡
አባቷ ያሳደጋትም በዚያ እምነት ጸንታ
እንድትኖር ነውና፤ በወሰደችው እርምጃ የተቃወሞ ድምጽ አላሰማችም፡፡
ነገሩን ውስጥ ውስጡን ስታብላላ ቆየችና......
“ሻምበል አደራህን! ትሁቴ ህጻን ልጅ ናት።እንደታላቅ ወንድም ተንከባከባት፡፡ እሷ ምኑንም የማታውቅ አንድ ፍሬ
ልጅ ናት፡፡ ለመጠንቀቁም ቢሆን አንተ ትሻላለህ፡፡ እሷ ምኑን ታውቀዋለች ብለህ
ነው?" የአሁኑ ስህተት እንዳይደገምና፤ በሌላ ጊዜ ተጨማሪ ጉዳት
እንዳይደርስባት፤ ሻምበል ሃላፊነቱን እንዲወጣ በማሳሰብ፤ አደራዋን
አጠበቀች፡፡ እሱም ትህትና ከሆስፒታል እንደወጣች ይዟት እንደሚመጣ
ቃል ገባላት፡፡ በመጠኑም ቢሆን ልቧ ትንሽ እረፍት አገኘ፡፡
“የአንዱአለሜ ወሬስ ? ምነው ጭልጥ ብሎ ጠፋ?" አከታትላ ጠየቀችው፡፡
“እኔ ራሴ ካገኘሁት ሳምንት ሆኖኛል እማማ፡፡ ለፈተናው ዝግጅት ሸፍቷል፡፡ ዘንድሮ አንደኛ ካልወጣሁ ሰው አይደለሁም ሲል የፎከረውን ለመፈፀም ቆርጦ መነሳቱን ትህትና ነግራኛለች። ምንም አያስቡ፤ ፈተናውን እንደጨረሰ እንዲመጣ እነግረዋለሁ።” ምክንያቱ
ብዙ ባይዋጥላትም የሻምበልን የማፅናኛ ቃል ከማዳመጥ በስተቀር አማራጭ አልነበራትም፡፡ዝም አለች፡፡ ከዚያም ሻምበል በግማሽ ልቡ ሆኖ፤ የሆነ ያልሆነውን፤ ሲያወራት ከቆየ በኋላ፤ ተሰናብቷት ወደ ትህትና ሩጫውን ቀጠለ....
ትህትና የቀዶ ህክምና ከተደረገላት በኋላ በአንደኛ ማእረግ እንድትተኛ ያደረገው ሻምበል ብሩክ ነው፡፡ ሻምበል አስፈላጊውን ክፍያ በመፈጸም ንጽህናው በተጠበቀና፤ ተጨማሪ በሽተኛ በሌለበት
አንደኛ ማእረግ ውስጥ እንድትተኛ የፈለገበት ዋናው ምክንያት፤
በሚተኙ በሽተኞች ስቃይ ተጨማሪ የአእምሮ መረበሽ ሊደርስባት ይችላል በሚል ፍራቻ ነው፡፡
ለቀዶ ጥገናው የተወጋችው ማደንዘዣ ስራውን በማጠናቀቁ ለአስቸኳይ ህክምናው በተሰጣት በሀያ አራት ሰአት ውስጥ ከሰመመናዊ እንቅልፉ ነቃችና አይኗን ገለጥ አደረገችው፡፡ ጣሪያውን ተመለከተች፡፡ ዙሪያዋን ቃኘች
የት እንዳለች፤ ምን እንደሆነች፤ በፍጹም
አታውቀውም፡፡ የተወጋችው የእንቅልፍ
መርፌ ፤ በጥይት የቆሰለው ሰውነቷና
እንደ ጉድ የፈሰሰው ደሟ መላ
አካሏን ድቅቅ አድርጐታል፡፡ከግራ ጆሮዋ ጀምሮ ፊቷ በአጠቃላይ በፋሻ ተሸፍኗል፡፡በክንዷ ላይ የተሰካውን ግሉኮስ ተመለከተችው፡፡ ጠብ ጠብ... እያለ
ይወርዳል። እንደገና አይኗን ጨፈነች፡፡ትንሽ ቆየችና መልሳ ገለጠችው::
እንደገና በሀሳብ ባህር ውስጥ ገባች፡፡ ምን ነበር የሆነው ? የት ነው ያለችው? እዚህ ለምን መጣች? እሷ ማን ነች? ቆይ .. ቆ ይ.. ምን ነበር የሆነው ? የሆነ
ነገር ብዥ ፧ ብዥ አለባት እንዴ ?..
መርካቶ ውስጥ እንደሻውን... ከዚያ በኋላ እራሷን... እንዴ?
ምንድነው ነገሩ? እሷ ሞታለች አይደለም እንዴ? በሰማይ ቤት ነው ወይንስ በምድር ላይ ያለችው? በዚያች በተሰናበተቻት ምድር ላይ? በፍጹም ሊሆን አይችልም! እንቆቅልሹም ሊገባት አልቻለም፡፡ ከዚያም ፊት ለፊትዋ የተቀመጡትን ሰዎች ትኩር ብላ ተመለከተቻቸው፡፡
ብዥ ፤ ብ ዥ ፤አሉባት አላወቀቻቸውም :: እነሱ በሀዘን ተውጠው አይን አይኗን ይመለከቷታል፡፡ እንደገና ትኩር ብላ ከመታሸግ በተረፈው በቀኝ አይኗ አየቻቸው፡፡ አሁንም አላወቀቻቸውም፡፡ እንቅስቃሴ የላትም፡፡እዚያ ከፊት ለፊቷ ሆነው በሀዘን ኩርምት ጭብጥ ብለው የተቀመጡትን ሰዎች በድጋሜ በጥንቃቄ ተመለከተቻቸው፡፡ የሆነ ምስል መጣላት፡፡
የምታውቀው ምስል በርቀት የምታውቀው ምስል.. አዎን
ታውቃቸዋለች እንጂ !! እንዴ..? በሚገባ ታውቃቸዋለች :: ቀስ ብላ በለሆሳስ ተጣራች "ብ..ሩ. ኬ..... አ . ዜ. ቢ . ና
እህህህ....." በዚህ ጊዜ አዜብ ቀስ ብላ ተነሳችና ሄዳ አጠገቧ ቆመች፡፡ ብሩክም አዜብን ተከትሎ ወደ አልጋው ተጠጋ፡፡ሻምበል እንደዚያ ሆና ሊያያት አልቻለም :: እንባው አመለጠውና ቀስ ብሎ ጉንጮቹን
እያቋረጠ ፈሰሰ፡፡
“እ ማ ዬ...ደ ህ...ና. ነች? ..አ.ን.ዱ.ዬስ..?"
"ሁለቱም በጣም ደህና ናቸው፡፡ ስለ እነሱ ምንም አታስቢ፡፡ እኛ አለን፡፡ አሁን ዋናው ማሰብ ያለብሽ ስለራስሽ ጤንነት ብቻ ነው እሺ?” አዜብ ነበረች፡፡
“እ..ሺ በደከመ ድምጽ፡፡
“ትሁት አዜብ የምትልሽን ስሚያት፡፡ስለ እማማ ምንም የሚያስጨንቅሽ ነገር የለም፡፡እሳቸው አንቺ ስለጠፋሽባቸው ነው ትንሽ ያሰቡት እንጂ በጣም ደህና ናቸው፡፡ ቶሎ ድነሽ ሄደሽ እንዲያዩሽ
በሃሳብና በጭንቀት ራስሽን መጉዳት የለብሽም፡፡ እሺ? አንዱ አለምም ድኗል ማለት ይቻላል፡፡ሰሞኑን መጥቶ ይጠይቅሻል እሺ?” ጉንጮቿን
እየዳበሰ፡፡
እሺ” አለች በድጋሜ፡፡ በዚያው ድክምክም ባለ ድምጿ። አሉኝ የምትላቸውና የምትተማመንባቸው ሁለቱ ጓደኞቿ፤ ደራሾቿ ፤ በዚህ በክፉ ቀን እንኳ ከጐኗ
👍1
ሳይለዩ ፤ አጠገቧ ቆመው ተስፋ
ሲሰጧት፤ እናቷን የማየት ጉጉት፣ ወንድሟን በድጋሜ የማግኘትን
ፍላጎት፤ እንደገና የመኖርን ተስፋ፤ እነዚያ ዳግመኛ ላትመኛቸው የተሰናበተቻቸውን ነገሮች በድጋሜ ለማግኘት፤ ልቧ እንደ አዲስ ተመኘ፡፡
በዚሁ መካከል መርፌ የምትወጋበት ሰአት ስለደረሰ፣ ነርሷ መድሀኒት የያዘውን ጋሪ እየገፋች ወደ ክፍሉ ስትገባ፤ አዜብና ብሩክ ክፍሉን ለቀው ወጡ፡፡ ደግነቱ ሁለቱም ወንድምና እህት የተኙት እዚያው ጥቁር አንበሳ በመሆኑ፤ ለአስታማሚዎቻቸው ሩጫን ቀንሶላቸዋል..... አንዱ አለምን የምትንከባከበው አዜብ ነች፡፡ በተለይ ለዚህ ያበቃሁት እኔ ነኝ የሚል የጥፋተኝነት ስሜት ስለተሰማት፤ ይህንን
ስሜትዋን ለማስወገድ የማታዘጋጅለት የምግብ አይነት አልነበረም፡፡
እዚያ የካቲት አስራ ሁለት ሆስፒታል እየሄደች ከእናቷ ጋር ከመፋጠጥ
እዚሁ ሁለቱን ለመንከባከብ፤ ብሩክ ደግሞ ከሰራተኛዋ ጋር ሆኖ ወይዘሮ ሃመልማልን እንዲንከባከብ፤ ክፍፍሉን ያደረገችው እሷ ናት፡፡ሰራተኛዋ ጥሩ፧ ጥሩ፧ ምግብ እንድታደርስላት በማድረግ በኩል ግን ወደ ኋላ አላለችም፡፡ አንዱአለም አሁን እየዳነ ነው፡፡ በተለይ ሻምበል እዚያ ሆሰፒታል መጥቶ ከጠየቀው በኋላ ደስተኛነቱ በእጥፉ
ጨምሯል፡፡ ትህትና ራስ ደስታ ሆስፒታል ገብታ የጠፋችበትን ምክንያት አዜብ ከነገረችው በኋላ ፧ ሻምበልም ለጥቂት ቀናት የጠፋው በዚሁ ችግር ምክንያት መሆኑን ገመተ ። እህቱ በመጥፋቷ
ብትናፍቀውም፤ እሷን ተክታ አዜብ የምታደርግለት እንክብክቤ ከፍተኛ
በመሆኑም ተፅናንቷል፡፡ አዜብ ለደረሰበት አደጋ ዋና ምክንያት ራሷን አድርጋ ስለቆጠረች ቶሎ ድኖ እንዲወጣ የማታደርገው ጥረት አልነበረም፡፡ ቆንጆ ምግብ አዘጋጅታ ትመጣና፤ እዚያ እጎኑ እቅፉ ስር ገብታ ስታጎርሰው ፤ ከዚያም አፉ ላይ የሚቀረውን ምግብ
ልታፀዳዳለት ከንፈሮቹን እብስ ፤ እብስ ስታደርጋቸው፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ሄዳ ከአንገቱ ቀና በማድረግ፤ በክንዷ ላይ ጣል ታደርገውና አጥሚት ስታጠጣው ፤ ከዚያም ራቁት ክንዷ ራቁት ክንዱን
ሲያሞቀው፡፡ ከዚያም ስውነቱን ሲግል ! በዚያ የግለት ስሜት የተነሳ ደግሞ ከዚያ በፊት ስለሷ አንድም ጊዜ ተሰምቶት የማያውቅ ፆታዊ ንዝረት ሲነዝረው፤ በተለይ ደግሞ አስተያየቷ ... አይን አይኑን
በስስት እያየች፤ ስልምልም፤ ስልምልም... ስትልበት፡፡ ይሄ ሁኔታ በየጊዜው እየተደጋገመ ሲመጣ ፤ ለሷ የተለየ
ስሜት እያሳደረ መጣ፡፡ ትኩር ብሎ ሲመለከታት ይቆይና ለራሱ ግርም ይለው ጀመር አዜብ እንደዚህ ቆንጆ ነበረች እንዴ ? በማለት ራሱን ደጋግሞ ጠየቀ፡፡
እንዴት አይነት ተአምር ነው ? ግን አዜብ እንደዚህ ታምር ነበረ? ለምንድነው እስከዛሬ ድረስ እንደዚህ ቆንጆ መሆንዋን ያላየሁት? አቤት ስትስቅ ደግሞ እንዴት ያምርባታል? ጥርሶችዋ እንደዚህ ያምሩ ነበረ? እስከዛሬ ድረስ እንዴት አላየኋቸውም? የታላቅ እህቴ ጓደኛ ስለሆነች እንደ እህቴ ቆጥሪያት አላየኋትም ነበር ማለት ነው ? ጓደኛዋ ብትሆን ታዲያ ምን ነበረበት? ጓደኝነታቸው የበለጠ ይዳብራል እንጂ፤ ይቀንሳል እንዴ? ራሱን በጥያቄ ያዋክብ ጀመር፡፡ አዜብም እንደዚያ አጠገቡ ሆና
ስታጫውተው ፣ ስታሳስቀው፤ ስትደባብስው፤ ስታጐርሰው፤ በክንዷ ላይ
ጣል አድርጋ፤ እህል ውሃ ስታቀማምሰው፤ ጠረን ለጠረን ሲለዋወጡ፡ ሲለማመዱ
ቀስ በቀስ እሷም ስለ አንዱአለም በልቧ ጥያቄዎችን በማነሳሳት እራሷን መጠየቅ ጀመረች፡፡ እንዴት እስከዛሬ ድረስ የዚህ
አይነት ስሜት ሳይሰማኝ ቀረ? በማለት ተገረመች .ስንቱን የምታተረማምሰዋ ሴትዮ አንዱአለምን የመሰለ ውብ ልጅ ለመቅመስ እንዴት እንዳልቀደመች ደነቃት :: የጓደኛዬ ወንድም ስለሆነ ነው ወይንስ
እንደዚህ እንደአሁኑ አይነት አጋጣሚ ተፈጥሮ ተቀራርበን፡ ተጠጋግተን፡
ጠረን ለጠረን መለዋወጥ ባለመቻላችን? አንዱ አለም እኮ የሚፈቀር ልጅ
ነው፡፡ ወይ ጉድ? ..ይህንን የውስጥ ፍላጐታቸውን በአንደበታቸው
አያውጡት እንጂ አንዳንድ ድርጊታቸው ስለሚመሰክር ልብ ለልብ እየተግባቡ መጡ፡፡ አንዳንድ ጊዜ በድንገት አይኖቻቸው ሲጋጩ ድንግጥ የማለት፡ የልባቸው ምት የመጨመር፡ የስሜት መለዋወጥ፣ ይሄና ይሄንን የመሳሰሉ ክስተቶች ተደጋገሙ፡፡ በዚያን እለት አንዱ
አለም ከጐኑ ያለው በሽተኛ መተኛቱን ሲያረጋግጥ፤ የሚያጎርሰው : የሚዳብሰው፡ የቀኝ እጇን መዳፍ ወደ ደረደቱ አስጠጋና ገልብጦ ውስጡን በስሱ ከዳሰስ በኋላ ፤ ቀስ ብሎ ሳመው :: በዚ ጊዜ ቀልጣፋዋ ልጅ ጊዜ አላጠፋችም፡፡ ከሱ ይህንን ያክል ፍንጭ
ካገኘች በቂ ነው :: እሷም ቀስ አለችና የውስጥ መዳፉን ሳም አደረገችለት፡፡ ከዚያም ወደ ደረቱ ትንሽ ሳብ ሲያደርጋት የገፈተሯትን ያህል ሄዳ ደረቱ ላይ ቀስ ብላ ወደቀችና ፤ ሰው ሳይመጣ ፤ ከንፈሩን
ሳም አደረገችው፡፡ እሱም ሳማት፡፡ መሳም ብቻ ሳይሆን በደንብ አድርጉ መጠጣት፡፡ ጣፈጠችው፡፡ ጣፈጣት፡፡ ፍቅር ተጀመረች፡፡ ከዚያ በኋላማ መነፋፈቅ፡ መቅበጥበጥ : ሲገናኙ ምኑ ይጠየቃል ? ትንሽ ሲለያዩ ፍዝዝ እያሉ መተያየት፡ መደባበስ ሆነ ስራቸው፡፡ ትህትና ከጊዜ ወደ ጊዜ ጤናዋ እየተሻሻለ መጣ :: አዜብና ሻምበል ብሩክ ከላይ እታች በማለት የሚደረገውን ሁሉ እያደረጉ ናቸው፡፡ የእንደሻው ወላጆች
እነሱ ለትህትና ህይወት " እንደዚያ ሲሯሯጡ ፤ ደግሞ የልጃቸውን ህይወት ለማትረፍ ከላይ እታች እየተሯሯጡ ብቻም
ሳይሆን፤ እየተራወጡ፤ ናቸው፡፡ የእንደሻው ጉዳት ከባድ ነበር፡፡ በተለይ....
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ሲሰጧት፤ እናቷን የማየት ጉጉት፣ ወንድሟን በድጋሜ የማግኘትን
ፍላጎት፤ እንደገና የመኖርን ተስፋ፤ እነዚያ ዳግመኛ ላትመኛቸው የተሰናበተቻቸውን ነገሮች በድጋሜ ለማግኘት፤ ልቧ እንደ አዲስ ተመኘ፡፡
በዚሁ መካከል መርፌ የምትወጋበት ሰአት ስለደረሰ፣ ነርሷ መድሀኒት የያዘውን ጋሪ እየገፋች ወደ ክፍሉ ስትገባ፤ አዜብና ብሩክ ክፍሉን ለቀው ወጡ፡፡ ደግነቱ ሁለቱም ወንድምና እህት የተኙት እዚያው ጥቁር አንበሳ በመሆኑ፤ ለአስታማሚዎቻቸው ሩጫን ቀንሶላቸዋል..... አንዱ አለምን የምትንከባከበው አዜብ ነች፡፡ በተለይ ለዚህ ያበቃሁት እኔ ነኝ የሚል የጥፋተኝነት ስሜት ስለተሰማት፤ ይህንን
ስሜትዋን ለማስወገድ የማታዘጋጅለት የምግብ አይነት አልነበረም፡፡
እዚያ የካቲት አስራ ሁለት ሆስፒታል እየሄደች ከእናቷ ጋር ከመፋጠጥ
እዚሁ ሁለቱን ለመንከባከብ፤ ብሩክ ደግሞ ከሰራተኛዋ ጋር ሆኖ ወይዘሮ ሃመልማልን እንዲንከባከብ፤ ክፍፍሉን ያደረገችው እሷ ናት፡፡ሰራተኛዋ ጥሩ፧ ጥሩ፧ ምግብ እንድታደርስላት በማድረግ በኩል ግን ወደ ኋላ አላለችም፡፡ አንዱአለም አሁን እየዳነ ነው፡፡ በተለይ ሻምበል እዚያ ሆሰፒታል መጥቶ ከጠየቀው በኋላ ደስተኛነቱ በእጥፉ
ጨምሯል፡፡ ትህትና ራስ ደስታ ሆስፒታል ገብታ የጠፋችበትን ምክንያት አዜብ ከነገረችው በኋላ ፧ ሻምበልም ለጥቂት ቀናት የጠፋው በዚሁ ችግር ምክንያት መሆኑን ገመተ ። እህቱ በመጥፋቷ
ብትናፍቀውም፤ እሷን ተክታ አዜብ የምታደርግለት እንክብክቤ ከፍተኛ
በመሆኑም ተፅናንቷል፡፡ አዜብ ለደረሰበት አደጋ ዋና ምክንያት ራሷን አድርጋ ስለቆጠረች ቶሎ ድኖ እንዲወጣ የማታደርገው ጥረት አልነበረም፡፡ ቆንጆ ምግብ አዘጋጅታ ትመጣና፤ እዚያ እጎኑ እቅፉ ስር ገብታ ስታጎርሰው ፤ ከዚያም አፉ ላይ የሚቀረውን ምግብ
ልታፀዳዳለት ከንፈሮቹን እብስ ፤ እብስ ስታደርጋቸው፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ሄዳ ከአንገቱ ቀና በማድረግ፤ በክንዷ ላይ ጣል ታደርገውና አጥሚት ስታጠጣው ፤ ከዚያም ራቁት ክንዷ ራቁት ክንዱን
ሲያሞቀው፡፡ ከዚያም ስውነቱን ሲግል ! በዚያ የግለት ስሜት የተነሳ ደግሞ ከዚያ በፊት ስለሷ አንድም ጊዜ ተሰምቶት የማያውቅ ፆታዊ ንዝረት ሲነዝረው፤ በተለይ ደግሞ አስተያየቷ ... አይን አይኑን
በስስት እያየች፤ ስልምልም፤ ስልምልም... ስትልበት፡፡ ይሄ ሁኔታ በየጊዜው እየተደጋገመ ሲመጣ ፤ ለሷ የተለየ
ስሜት እያሳደረ መጣ፡፡ ትኩር ብሎ ሲመለከታት ይቆይና ለራሱ ግርም ይለው ጀመር አዜብ እንደዚህ ቆንጆ ነበረች እንዴ ? በማለት ራሱን ደጋግሞ ጠየቀ፡፡
እንዴት አይነት ተአምር ነው ? ግን አዜብ እንደዚህ ታምር ነበረ? ለምንድነው እስከዛሬ ድረስ እንደዚህ ቆንጆ መሆንዋን ያላየሁት? አቤት ስትስቅ ደግሞ እንዴት ያምርባታል? ጥርሶችዋ እንደዚህ ያምሩ ነበረ? እስከዛሬ ድረስ እንዴት አላየኋቸውም? የታላቅ እህቴ ጓደኛ ስለሆነች እንደ እህቴ ቆጥሪያት አላየኋትም ነበር ማለት ነው ? ጓደኛዋ ብትሆን ታዲያ ምን ነበረበት? ጓደኝነታቸው የበለጠ ይዳብራል እንጂ፤ ይቀንሳል እንዴ? ራሱን በጥያቄ ያዋክብ ጀመር፡፡ አዜብም እንደዚያ አጠገቡ ሆና
ስታጫውተው ፣ ስታሳስቀው፤ ስትደባብስው፤ ስታጐርሰው፤ በክንዷ ላይ
ጣል አድርጋ፤ እህል ውሃ ስታቀማምሰው፤ ጠረን ለጠረን ሲለዋወጡ፡ ሲለማመዱ
ቀስ በቀስ እሷም ስለ አንዱአለም በልቧ ጥያቄዎችን በማነሳሳት እራሷን መጠየቅ ጀመረች፡፡ እንዴት እስከዛሬ ድረስ የዚህ
አይነት ስሜት ሳይሰማኝ ቀረ? በማለት ተገረመች .ስንቱን የምታተረማምሰዋ ሴትዮ አንዱአለምን የመሰለ ውብ ልጅ ለመቅመስ እንዴት እንዳልቀደመች ደነቃት :: የጓደኛዬ ወንድም ስለሆነ ነው ወይንስ
እንደዚህ እንደአሁኑ አይነት አጋጣሚ ተፈጥሮ ተቀራርበን፡ ተጠጋግተን፡
ጠረን ለጠረን መለዋወጥ ባለመቻላችን? አንዱ አለም እኮ የሚፈቀር ልጅ
ነው፡፡ ወይ ጉድ? ..ይህንን የውስጥ ፍላጐታቸውን በአንደበታቸው
አያውጡት እንጂ አንዳንድ ድርጊታቸው ስለሚመሰክር ልብ ለልብ እየተግባቡ መጡ፡፡ አንዳንድ ጊዜ በድንገት አይኖቻቸው ሲጋጩ ድንግጥ የማለት፡ የልባቸው ምት የመጨመር፡ የስሜት መለዋወጥ፣ ይሄና ይሄንን የመሳሰሉ ክስተቶች ተደጋገሙ፡፡ በዚያን እለት አንዱ
አለም ከጐኑ ያለው በሽተኛ መተኛቱን ሲያረጋግጥ፤ የሚያጎርሰው : የሚዳብሰው፡ የቀኝ እጇን መዳፍ ወደ ደረደቱ አስጠጋና ገልብጦ ውስጡን በስሱ ከዳሰስ በኋላ ፤ ቀስ ብሎ ሳመው :: በዚ ጊዜ ቀልጣፋዋ ልጅ ጊዜ አላጠፋችም፡፡ ከሱ ይህንን ያክል ፍንጭ
ካገኘች በቂ ነው :: እሷም ቀስ አለችና የውስጥ መዳፉን ሳም አደረገችለት፡፡ ከዚያም ወደ ደረቱ ትንሽ ሳብ ሲያደርጋት የገፈተሯትን ያህል ሄዳ ደረቱ ላይ ቀስ ብላ ወደቀችና ፤ ሰው ሳይመጣ ፤ ከንፈሩን
ሳም አደረገችው፡፡ እሱም ሳማት፡፡ መሳም ብቻ ሳይሆን በደንብ አድርጉ መጠጣት፡፡ ጣፈጠችው፡፡ ጣፈጣት፡፡ ፍቅር ተጀመረች፡፡ ከዚያ በኋላማ መነፋፈቅ፡ መቅበጥበጥ : ሲገናኙ ምኑ ይጠየቃል ? ትንሽ ሲለያዩ ፍዝዝ እያሉ መተያየት፡ መደባበስ ሆነ ስራቸው፡፡ ትህትና ከጊዜ ወደ ጊዜ ጤናዋ እየተሻሻለ መጣ :: አዜብና ሻምበል ብሩክ ከላይ እታች በማለት የሚደረገውን ሁሉ እያደረጉ ናቸው፡፡ የእንደሻው ወላጆች
እነሱ ለትህትና ህይወት " እንደዚያ ሲሯሯጡ ፤ ደግሞ የልጃቸውን ህይወት ለማትረፍ ከላይ እታች እየተሯሯጡ ብቻም
ሳይሆን፤ እየተራወጡ፤ ናቸው፡፡ የእንደሻው ጉዳት ከባድ ነበር፡፡ በተለይ....
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2😁1
#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
...ማሰብና መጀመር የተለያዩ ሆነውበት ተቸግሯል አቤል ። ሐሳቡ በጣም ይመጥቅበታል ።ሊጽፍ ያሰበው ነገር መጽሐፍ ይሆንበታል ። ለሐሳቡ ወግ የሚያግኝለትም አይመስለው ። ወረቀቱን ይዞ ቁጭ ሲል ግን ከብዕሩ ጠብ የሚል ነገር ይጠፋል ። ባዶ ወረቀት ላይ ማን ፎር ሂምሰልፍ” ከሚል አርዕስት ጋር መፋጠጥ ብቻ !
“ችግሩ ከቋንቋው ይሆን ? ” ሲል አሰበ ። በሰው ቋንቋ ከምቸገር ሓሳቤን እንደ ልቤ ላንቆረቁርበት በምችለው በራሴ ቋንቋ ለምን አልፅፍም?።
ባዶውን ወረቀት ከአጠገቡ አገለለና መጽሐፍ ገለጠ ለጽሑፉ የሚጠቅመውትን መጽሐፎች መርጦ አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ ከምሯል ። መጻፍ ከመጀመሩ በፊት በዚህ አርዕስት
ጐዳይ ላይ የተጻፉ ብዙ መጽሐፎች ማንበብ እንዳለበት ስለ ተረዳ፡ ሰሞኑን እያነበበ ነበር። ችግሩ ግን አለ ከሚያነበው መጽሐፍ ላይ ብዙ ሰዓት መቆየት አለ መቻሉ ነው ከመጽሐፉ ውስጥ ጠቃሚ ሐሳብ ሲያገኝ የእሱ ሐሳብ ቀድሞ ይሐጥቅና ጻፍ ጻፍ ይለዋል
አሁንም ከተቀመጠበት ተነሥቶ ትንሽ ተንጎራደደ ። ከመንጐራደዱ ጋርም የሚጽፈው ነገር ብልጭ አለለት
ሰው ከራሱ ጋር የሚጣላው ለምንድነው ? በግል ምኞትና ግብ አእምሮው ተወጥሮ ሲጨነቅ ነው ። ነገር ግን የሰው ልጅ የመጨረሻ ግቡ እኛ እንጂ እኔ መሆን የለበትም ከራሱ ጋር ሊታረቅ የሚችለው በዚህ እምነት ተጠምቆ ከግሉ ይልቅ ለማኅበራዊ ችግር ክብደት ሲሰጥና ደስታውን ከኅብረተሰቡ ጣፋጭ ሕይወት ውስጥ ለማግኘት ሲሞክር ነው ። ሰው በመጀመሪያ ለሕያውነቱ ከፍተኛ ግምት መስጠትና ማድነቅ አለበት ። ይህን ካመነ ደግም ማናቸውም በውስጡ የሚከሠቱ ነገሮች የሕያውነቱ ነጸብራቆች ስለሆኑ
እንዳመጣጣቸው ተቀብሎ መፍታት እንጂ ለችግሮች ምረታት የለበትም ። ሰው በትግሉ በተጸጥሮ ላይ ፍጹም የበላይነቱን መቀዳጀት አለበት ።
እቤል መጻፍ የፈለገውን መቋጠሪያ ሐሳብ ያገኝ መሰለው ደስ ደስ አለው። በአንጻሩ ግን ከውስጡ አዘናጊ ስሜት ይታግለው ነበር ። " አይ አቤል ፤ አሁንስ ጅል ሆንክ አዲስ ሐሳብ ያፈለቅክ መስሎህ ነው ? ስንት ፈላስፋዎች ብለውት ብለውት የበቃውን ነገር እንዴት እንደ አዲስ ታነሳዋለህ ? እባክህ ይልቅ ያልተሳበ አዲስ ነገር ፈልግ ።ለዚያውስ በዚህ ዓለም ላይ ምን ያልተባለ ነገር አለ ?”
አቤል የራሱ ስሜት አስጠላው ለምንድነው ስሜቱን ገንቢውን ትቶ አፍራሹ ላይ የሚሮጠው? አዲሱ ሰው ሁሉን ነገር “ ተብሏል” እያለ ራሱን የሚያዘናጋ ከሆነና እጁን አጣምሮ ከተቀመጠ ነገር ተበላሸ ከአሁን በፊትም ማንም ቢሆን ፍጹም አዲስ ነግር ይዞ አልተሄዶም ። ሁሉም እውቀቱን የቀመረው በተከሠረት ወይም በተባለ ነገር ላይ እየቆመ ነው።እና አቤል አቤልሽ ! ይልቅ ደፍረህ ጀምር የአቅምህን ሞክር ፤ ጫር ! ” አለና እንደገና ቁጭ አለ።
እንዴት እንደሚጀምረው ቁልጭ ብሎ ታየው " ሰፊ አርዕስት ነው የያዘው ፤ስለዚህ በንዑስ ርዕስ ከፋፍሎ እያንዳንዷን ንዑስ ክፍል በጽሑፍ ማስረጃና በሕይወት ገጠመኝ
አስደግፎ ማስኬድ ! ሰውነቱን አንዳች የደስታ ስሜት ወረረው ። ሐሳቡ ካለበት መጥቆ ሲሮጥ ንዑስ ርዕሱ ልጓም ሆኖ
ያዘለት ። ሰው የራሱ ወዳጅ የሚሆንበትን ሐሳብ ከመደርደሩ በፊት ከራሱ ጋር የሚጣላባቸውን ሁኔታዎች ለመደርደር ተገደደ ። እዚህ ላይ ለመድረስ ደግሞ፥ ሰው በተፈጥሮ ይዟቸው የሚወጣውንና ከአካባቢው የሚቀስማቸውን ዐብይት ጸባያት ይዞ መነሣት ነበረበት ። የጅማሬ ሐሳቡን በዚህ ንዑስ ርዕስ ሥር አጠቃልሎ ፥ “ በዚህ ዓለም ላይ ታላቅና
ክቡር ፍጡር ነው” ሲል ጀመረ ።
በተመስጦ እየጻፈና ደጋፊ ሐሳቦች ፍለጋ መጽሐፎች እያገላበጠ ትንሽ እንደ ቆየ ፡ ሞኒካ ሻይ ይዛለት መጣች።
የአምስት ሰዓት ሻይ ነበር ። ጊዜው ከምኔው እንደ ሮጠ ገረመው
“ ጽሑፉን ጀመርኩት “ ኮ ” አላት ፡ ገና እየገባች ሳለች ።
“ ዳስ ኢስት ሸን ” አለችው ሞኒካ • ፈገግ ብላ ደስታዋን በመግለጽ ።
አቤል ይህንኑ “ ጀመርኩት ” የሚለውን ቃል ለዮናታንም ለመንገር ተቻኮለ ። እንዲያመጡለት የጠየቃቸውን የቀድሞ የተበላሹ የጥናት ጽሑፎቹን ባመጡለት ጊዜ ፥ የገባላቸው ቃል ትዝ አለው ። ወረቀቶቹን ተቀብሎ ፊታቸው በክ
ብሪት ካቃጠለ በኋላ ፥ አሁን ከፊትዎ የቆመው አዲሱ አቤል ነው ። አዲስ ጽሑፍ አዘጋጅቶ ያሳይዎታል ” ብሏ
ቸው ነበር ። አሁን ዮናታን የሚመጡበት የምሳ ሰዓት ራቀበት።
ሞኒካ አሁን እቤል ያለበትን ጥሩ ስሜት ካረጋገጠች በኋላ፥ ወደ መኝታ ክፍሏ ሔዳ አንድ ጉርድ ፎቶግራፍና የታሸገ
ኢንቬሎፕ ይዛ ተመለሰች ።
“ ይህችን ልጅ ታውቃታለህ ? ” አለችው ፥ ፎቶውን ዐይኑ ሥር አቅርባ ።ፉት ብሎ የነበረውን ሻይ ቶሎ መዋጥ አቃተው
የልብ ትርታ የሚቀሰቅስ ምስል ! አስደንግጦ የሚያስደስት ምስል ! “ ማወቅ ብቻ ነው!? አምልኬባታለሁ እንጂ!” ሊላት ፈለገ። የሞኒካ ቶሎ መልስ መፈለግ ግን፥ አቤል ነገሩን አመዛዝኖ እንዲናገር ጊዜ አልሰጠውም ።
አዎ ! አላት ፥ ሌላውን ስሜቱን ዋጥ አድርጎ
“ የት ? ”
“ ዩኒቨርስቲ ውስጥ አንድ ሴሚስተር ሙሉ በዐይን ፍቅር የማቀቅኩላት ናት” አላት ቃናው በተለወጠ ድምፅ ።
“ ከዚህ ፎቶዋ ጋር ደብዳቤ ልካልሃለች ” አለችና የታሸገውን ፖስታ ሰጠችው። ፈጥኖ ተቀበላት ። ነገር ግን ፈጥኖ መቅደድ አልቻለም ። አንዳች ነገር እጁን የያዘው ይመስል ተንቀጠቀጠ ።
በሚያነብበት ጊዜ ነጻ እንዲሆን በማሰብ ሞኒካ ክፍሉን ለቅቃለት ወጣች ። ደብዳቤዉንና ፎቶዉን ከእስክንድር
ከተቀበሰች ሁለት ቀን አልፎአል ።ለአቤል ወድያውኑ ያልሰጠችው እንዲህ ጥሩ ስሜት እስኪታይበት በመጠበቅ ነበር።
አቤል ደብዳቤዉን ግልጾ ማንበብ ጀመረ፡-
አቤል፥ ስምህን ደብዳቤ ላይ ለመጀሪያ ጊዜ ስጽፈው የተሰማኝን ስሜት ልገልጽልህ አልችልም ። የምወደውንና
የምፈልጎውን ቃል መጥራት ለምን እንደሚያስፈራኝ ሊገባኝ አልቻለም ። የዚህን ደብዳቤ ረቂቅ ብታየው ትግረማለህ ። ስርዝ፤ ድልዝዝ ብቻ ነው። ከስሜቴ ጋር ክፉኛ መታገሌን በዚህ መገመት ትችላለህ ።
ይህን ደብዳቤ እንድጽፍልህ ያደፋፈረኝ እስክንድር ነው ። ጥሩ ጓደኛ ነው ያለህ እሱ ባይገፋፋኝ ኖሮ እንዲሁ ስሜቴን አምቄ ውስጥ ውስጤን እሠቃያለሁ እንጂ ከቶም አልሞክረውም ነበር ። አንተ በእኔ የተነሣ የተቀበልከውን ስቃይ ስሰማ ለብቻዬ ተደብቄ ስቅስቅ ብዬ ነው ያለቀስኩት ፤ግን ጥፋተኛው ማን ነው ? አየህ አቤል ! እኔ መቼም ሴት ነኝ ፤ደፍሬ መጥቼ እንዳነጋግርህ የአካባቢ ተጽዕኖ
አለብኝ ። አንተ ግን በሩቅ ከምትሠቃይ ቀርበህ ! ብታነጋረኝና እወድሻለሁ ብትለኝ ምን ነበረበት ።
“ሕመምህ ጠልቆ የተሰማኝ አሁን ነው ። ለካስ ፍቅር ተገጣጥሞ ካልሰመረ ሥቃይ ነው። በካምፓስ ውስጥ አንተን በዐይኔ ካጣሁበት ጊዜ ጀምሮ ያለሁበትን ሁኔታ ልገልጽልህ አልችልም ። አንተን ለማየት እናፍቃለሁ ፣ ብቸኝነት ያሰቃየኛል ፥ አካባቢዩ ያስጠላኛል ፤ጥናት ያንገሸግሸኛል ፣ሁሉ ነገር ከብዶና መርሮ ይታየኛል ። እውነቴን ነው የምልህ
የተፈጥሮ ክሥተት ባይሆን ኖሮ፡ አፍላ ፍቅር ፈጽሞ እያስመኝም
“ በመጀመሪያው ሴሚስተር ከትምህርቴ እንዳልሰናከል እፈራ ስለ ነበር፡ ፍቅርህን ክፉኛ ተቃውሜዋለሁ›
አሁን የተረዳሁት ነገር ቢኖር ግን ፥ ፍቅር ታግለው የሚጥሉት ነገር አለመሆኑን ነው ። ገና መጀመሪያ የዩኒቨርስቲውን ግቢ ስረግጥ ካየኸኝ ጀምሮ በዐይን እንደምትከተለኝ ያልተረዳሁልህ እንዳይመስልህ እያንዳንዷ እይታ ከንግግር የበለጠ ተሰምታኛለች። እንዲያውም አንዳንዴ ቃላት
፡
፡
#ክፍል_ሃምሳ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
...ማሰብና መጀመር የተለያዩ ሆነውበት ተቸግሯል አቤል ። ሐሳቡ በጣም ይመጥቅበታል ።ሊጽፍ ያሰበው ነገር መጽሐፍ ይሆንበታል ። ለሐሳቡ ወግ የሚያግኝለትም አይመስለው ። ወረቀቱን ይዞ ቁጭ ሲል ግን ከብዕሩ ጠብ የሚል ነገር ይጠፋል ። ባዶ ወረቀት ላይ ማን ፎር ሂምሰልፍ” ከሚል አርዕስት ጋር መፋጠጥ ብቻ !
“ችግሩ ከቋንቋው ይሆን ? ” ሲል አሰበ ። በሰው ቋንቋ ከምቸገር ሓሳቤን እንደ ልቤ ላንቆረቁርበት በምችለው በራሴ ቋንቋ ለምን አልፅፍም?።
ባዶውን ወረቀት ከአጠገቡ አገለለና መጽሐፍ ገለጠ ለጽሑፉ የሚጠቅመውትን መጽሐፎች መርጦ አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ ከምሯል ። መጻፍ ከመጀመሩ በፊት በዚህ አርዕስት
ጐዳይ ላይ የተጻፉ ብዙ መጽሐፎች ማንበብ እንዳለበት ስለ ተረዳ፡ ሰሞኑን እያነበበ ነበር። ችግሩ ግን አለ ከሚያነበው መጽሐፍ ላይ ብዙ ሰዓት መቆየት አለ መቻሉ ነው ከመጽሐፉ ውስጥ ጠቃሚ ሐሳብ ሲያገኝ የእሱ ሐሳብ ቀድሞ ይሐጥቅና ጻፍ ጻፍ ይለዋል
አሁንም ከተቀመጠበት ተነሥቶ ትንሽ ተንጎራደደ ። ከመንጐራደዱ ጋርም የሚጽፈው ነገር ብልጭ አለለት
ሰው ከራሱ ጋር የሚጣላው ለምንድነው ? በግል ምኞትና ግብ አእምሮው ተወጥሮ ሲጨነቅ ነው ። ነገር ግን የሰው ልጅ የመጨረሻ ግቡ እኛ እንጂ እኔ መሆን የለበትም ከራሱ ጋር ሊታረቅ የሚችለው በዚህ እምነት ተጠምቆ ከግሉ ይልቅ ለማኅበራዊ ችግር ክብደት ሲሰጥና ደስታውን ከኅብረተሰቡ ጣፋጭ ሕይወት ውስጥ ለማግኘት ሲሞክር ነው ። ሰው በመጀመሪያ ለሕያውነቱ ከፍተኛ ግምት መስጠትና ማድነቅ አለበት ። ይህን ካመነ ደግም ማናቸውም በውስጡ የሚከሠቱ ነገሮች የሕያውነቱ ነጸብራቆች ስለሆኑ
እንዳመጣጣቸው ተቀብሎ መፍታት እንጂ ለችግሮች ምረታት የለበትም ። ሰው በትግሉ በተጸጥሮ ላይ ፍጹም የበላይነቱን መቀዳጀት አለበት ።
እቤል መጻፍ የፈለገውን መቋጠሪያ ሐሳብ ያገኝ መሰለው ደስ ደስ አለው። በአንጻሩ ግን ከውስጡ አዘናጊ ስሜት ይታግለው ነበር ። " አይ አቤል ፤ አሁንስ ጅል ሆንክ አዲስ ሐሳብ ያፈለቅክ መስሎህ ነው ? ስንት ፈላስፋዎች ብለውት ብለውት የበቃውን ነገር እንዴት እንደ አዲስ ታነሳዋለህ ? እባክህ ይልቅ ያልተሳበ አዲስ ነገር ፈልግ ።ለዚያውስ በዚህ ዓለም ላይ ምን ያልተባለ ነገር አለ ?”
አቤል የራሱ ስሜት አስጠላው ለምንድነው ስሜቱን ገንቢውን ትቶ አፍራሹ ላይ የሚሮጠው? አዲሱ ሰው ሁሉን ነገር “ ተብሏል” እያለ ራሱን የሚያዘናጋ ከሆነና እጁን አጣምሮ ከተቀመጠ ነገር ተበላሸ ከአሁን በፊትም ማንም ቢሆን ፍጹም አዲስ ነግር ይዞ አልተሄዶም ። ሁሉም እውቀቱን የቀመረው በተከሠረት ወይም በተባለ ነገር ላይ እየቆመ ነው።እና አቤል አቤልሽ ! ይልቅ ደፍረህ ጀምር የአቅምህን ሞክር ፤ ጫር ! ” አለና እንደገና ቁጭ አለ።
እንዴት እንደሚጀምረው ቁልጭ ብሎ ታየው " ሰፊ አርዕስት ነው የያዘው ፤ስለዚህ በንዑስ ርዕስ ከፋፍሎ እያንዳንዷን ንዑስ ክፍል በጽሑፍ ማስረጃና በሕይወት ገጠመኝ
አስደግፎ ማስኬድ ! ሰውነቱን አንዳች የደስታ ስሜት ወረረው ። ሐሳቡ ካለበት መጥቆ ሲሮጥ ንዑስ ርዕሱ ልጓም ሆኖ
ያዘለት ። ሰው የራሱ ወዳጅ የሚሆንበትን ሐሳብ ከመደርደሩ በፊት ከራሱ ጋር የሚጣላባቸውን ሁኔታዎች ለመደርደር ተገደደ ። እዚህ ላይ ለመድረስ ደግሞ፥ ሰው በተፈጥሮ ይዟቸው የሚወጣውንና ከአካባቢው የሚቀስማቸውን ዐብይት ጸባያት ይዞ መነሣት ነበረበት ። የጅማሬ ሐሳቡን በዚህ ንዑስ ርዕስ ሥር አጠቃልሎ ፥ “ በዚህ ዓለም ላይ ታላቅና
ክቡር ፍጡር ነው” ሲል ጀመረ ።
በተመስጦ እየጻፈና ደጋፊ ሐሳቦች ፍለጋ መጽሐፎች እያገላበጠ ትንሽ እንደ ቆየ ፡ ሞኒካ ሻይ ይዛለት መጣች።
የአምስት ሰዓት ሻይ ነበር ። ጊዜው ከምኔው እንደ ሮጠ ገረመው
“ ጽሑፉን ጀመርኩት “ ኮ ” አላት ፡ ገና እየገባች ሳለች ።
“ ዳስ ኢስት ሸን ” አለችው ሞኒካ • ፈገግ ብላ ደስታዋን በመግለጽ ።
አቤል ይህንኑ “ ጀመርኩት ” የሚለውን ቃል ለዮናታንም ለመንገር ተቻኮለ ። እንዲያመጡለት የጠየቃቸውን የቀድሞ የተበላሹ የጥናት ጽሑፎቹን ባመጡለት ጊዜ ፥ የገባላቸው ቃል ትዝ አለው ። ወረቀቶቹን ተቀብሎ ፊታቸው በክ
ብሪት ካቃጠለ በኋላ ፥ አሁን ከፊትዎ የቆመው አዲሱ አቤል ነው ። አዲስ ጽሑፍ አዘጋጅቶ ያሳይዎታል ” ብሏ
ቸው ነበር ። አሁን ዮናታን የሚመጡበት የምሳ ሰዓት ራቀበት።
ሞኒካ አሁን እቤል ያለበትን ጥሩ ስሜት ካረጋገጠች በኋላ፥ ወደ መኝታ ክፍሏ ሔዳ አንድ ጉርድ ፎቶግራፍና የታሸገ
ኢንቬሎፕ ይዛ ተመለሰች ።
“ ይህችን ልጅ ታውቃታለህ ? ” አለችው ፥ ፎቶውን ዐይኑ ሥር አቅርባ ።ፉት ብሎ የነበረውን ሻይ ቶሎ መዋጥ አቃተው
የልብ ትርታ የሚቀሰቅስ ምስል ! አስደንግጦ የሚያስደስት ምስል ! “ ማወቅ ብቻ ነው!? አምልኬባታለሁ እንጂ!” ሊላት ፈለገ። የሞኒካ ቶሎ መልስ መፈለግ ግን፥ አቤል ነገሩን አመዛዝኖ እንዲናገር ጊዜ አልሰጠውም ።
አዎ ! አላት ፥ ሌላውን ስሜቱን ዋጥ አድርጎ
“ የት ? ”
“ ዩኒቨርስቲ ውስጥ አንድ ሴሚስተር ሙሉ በዐይን ፍቅር የማቀቅኩላት ናት” አላት ቃናው በተለወጠ ድምፅ ።
“ ከዚህ ፎቶዋ ጋር ደብዳቤ ልካልሃለች ” አለችና የታሸገውን ፖስታ ሰጠችው። ፈጥኖ ተቀበላት ። ነገር ግን ፈጥኖ መቅደድ አልቻለም ። አንዳች ነገር እጁን የያዘው ይመስል ተንቀጠቀጠ ።
በሚያነብበት ጊዜ ነጻ እንዲሆን በማሰብ ሞኒካ ክፍሉን ለቅቃለት ወጣች ። ደብዳቤዉንና ፎቶዉን ከእስክንድር
ከተቀበሰች ሁለት ቀን አልፎአል ።ለአቤል ወድያውኑ ያልሰጠችው እንዲህ ጥሩ ስሜት እስኪታይበት በመጠበቅ ነበር።
አቤል ደብዳቤዉን ግልጾ ማንበብ ጀመረ፡-
አቤል፥ ስምህን ደብዳቤ ላይ ለመጀሪያ ጊዜ ስጽፈው የተሰማኝን ስሜት ልገልጽልህ አልችልም ። የምወደውንና
የምፈልጎውን ቃል መጥራት ለምን እንደሚያስፈራኝ ሊገባኝ አልቻለም ። የዚህን ደብዳቤ ረቂቅ ብታየው ትግረማለህ ። ስርዝ፤ ድልዝዝ ብቻ ነው። ከስሜቴ ጋር ክፉኛ መታገሌን በዚህ መገመት ትችላለህ ።
ይህን ደብዳቤ እንድጽፍልህ ያደፋፈረኝ እስክንድር ነው ። ጥሩ ጓደኛ ነው ያለህ እሱ ባይገፋፋኝ ኖሮ እንዲሁ ስሜቴን አምቄ ውስጥ ውስጤን እሠቃያለሁ እንጂ ከቶም አልሞክረውም ነበር ። አንተ በእኔ የተነሣ የተቀበልከውን ስቃይ ስሰማ ለብቻዬ ተደብቄ ስቅስቅ ብዬ ነው ያለቀስኩት ፤ግን ጥፋተኛው ማን ነው ? አየህ አቤል ! እኔ መቼም ሴት ነኝ ፤ደፍሬ መጥቼ እንዳነጋግርህ የአካባቢ ተጽዕኖ
አለብኝ ። አንተ ግን በሩቅ ከምትሠቃይ ቀርበህ ! ብታነጋረኝና እወድሻለሁ ብትለኝ ምን ነበረበት ።
“ሕመምህ ጠልቆ የተሰማኝ አሁን ነው ። ለካስ ፍቅር ተገጣጥሞ ካልሰመረ ሥቃይ ነው። በካምፓስ ውስጥ አንተን በዐይኔ ካጣሁበት ጊዜ ጀምሮ ያለሁበትን ሁኔታ ልገልጽልህ አልችልም ። አንተን ለማየት እናፍቃለሁ ፣ ብቸኝነት ያሰቃየኛል ፥ አካባቢዩ ያስጠላኛል ፤ጥናት ያንገሸግሸኛል ፣ሁሉ ነገር ከብዶና መርሮ ይታየኛል ። እውነቴን ነው የምልህ
የተፈጥሮ ክሥተት ባይሆን ኖሮ፡ አፍላ ፍቅር ፈጽሞ እያስመኝም
“ በመጀመሪያው ሴሚስተር ከትምህርቴ እንዳልሰናከል እፈራ ስለ ነበር፡ ፍቅርህን ክፉኛ ተቃውሜዋለሁ›
አሁን የተረዳሁት ነገር ቢኖር ግን ፥ ፍቅር ታግለው የሚጥሉት ነገር አለመሆኑን ነው ። ገና መጀመሪያ የዩኒቨርስቲውን ግቢ ስረግጥ ካየኸኝ ጀምሮ በዐይን እንደምትከተለኝ ያልተረዳሁልህ እንዳይመስልህ እያንዳንዷ እይታ ከንግግር የበለጠ ተሰምታኛለች። እንዲያውም አንዳንዴ ቃላት
❤1👍1🥰1
መግለጽ የማይችሉትን ዐይን እንደሚናገር ተረድቻለሁ ።በተለይ ፥ ታስታውስ እንደሆነ እንድ ቀን እኔ ፡ ማርታና ቤተልሔም ከካምፓስ ወጥተን ስንሔድ ምን ያህል በቅናት ስሜት እንደ ተመለከትከኝ መቼም አልረሳውም ። አንተ ሌላ ቦታ የምንሔድ መስሉህ ሊሆን ይችላል ። ነገር ግን የሒድነው ሰርግ ቤት ተጠርተን ነበር። ታዲያ ያኔ የዋልኩት ውሎ ውሎ አይበለው ! በቅናት የተከተለኝ ዐይን ዐይኔ ውስጥ ቀርቶ ፥ ቀኑን ሙሉ ሲለበልበኝ ነው የዋለው ...
ይህን ሁሉ የምጽፈው የቆየ ቁስልህን ለመቀስቀስ አይደለም ። በአንድ በኩል ደብዳቤው በእርግጥ ከእኔ ከት ዕግሥት የተላከልህ መሆኑን እንድታምንበት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ስሜትህ ያልገባኝ ወይም ሥቃይህንን ያልተረዳሁልህ እንዳይመስልህ ነው ።
“ከላይ እንደ ገለጽኩልህ፡ችግሩን በመፍራት ፍቅርህን ታግዬ የማሸንፈው አልሆንኩም ። ብሞክረውም አንተን መርሳት ፍጹም የማይቻል ሙከራ ሆነብኝ። ምክንያቱም በአካባቢዬ ሴቶች ስለ አንተ ሲያወሩ በሰማሁ ቁጥር ስሜቴ ይቀሰቀሳል። ስምህን የሚያውቁት፡ “ ያ ጎበዙ ተማሪ” በሚል ቅጽል ነው የሚጠሩህ ። ይህ ቃል በእኔ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ነው ያሳደረብኝ ። በጉብዝናው በሚደነቅ ተማሪ መፈቀር ደስ ያሰኛል። ግን ደግሞ ግንኙነታችን ከዐይን አለ ማለፉን ሳመዛዝን ያበሽቀኛል ። ያ ሁሉ ዐልፎአል ። አሁን ስሜቴን አፍረጥርጨ ያወጣሁልህ ይመስለኛል ። አንተም ግልጽ ሁንልኝ ። ፍቅርን ሕመም ያደረግነው እኛው ነን ፤እባክህ ጐንለጐን ቁጭ ብለን አንተ በእኔ ፥ እኔ ባንተ እንደሰት ። ትምህርትህ በእኔ ምክንያት በመቋረጡ አዝናለሁ ። የምረዳህም
ሆን የምክስህ ነገር ቢኖር፡ ከወዲሁ ሙሉ ፈቃደኝነቴን እገልጽልሃለሁ ። በእኔ ግምት ካሳው ፍቅር ነው ፍቅሬን ሰጥቼህ ፍቅርህን ከመቀበል ሌላ ምን መፍትሔ ይኖራል ?
ያንተው ትዕግሥት አዳነ ”
አቤል ደብዳቤውን ሁለቴ አንብቦ በዝግታ አጠፈው ።እውስጡ ያነበበው የፍቅር ቃላትን ብቻ ሳይሆን እንባም ጭምር ነው ትዕግሥት ፊቷ በእንባ ሳይታጠብ ይህን
ደብዳቤ ጻፈች ማለት ዘበት ነው ። ጽሑፉን ያነበበ ሳይሆን ድምጿን የሰማ መሰለው ። ግን በእርግጥ ትዕግሥት እንዲህ ግልጽ ሆና የውስጧን የምትናገር ሴት ትሆን ? ማነው ጥፋተኛው ? ” የሚለው ቃል ታወሰውና፡ “እውነት ማነው?” ሲል አሰበ ። እሷንም ራሱንም ጥፋተኛ ማድረግ አልቻለም ። አንዲት የፍቅር ቃል እወድሻለሁ ብትለኝ ” ያለችው አንጀቱን በላው ። ነገር ግን ቃሏ አንድ መሆኗ ሳይሆን ክብደቷ ነው ለትዕግሥት ያልገባት ። ይህችን በፍቅረኛ ፊት መተንፈስ መቻል ምንኛ መታደል ነው !
ስለ እስክንድር አሰበ ። ለደብዳቤዉ መጻፍ ያደረገው ጥረት አስገረመው ። ከአሁን በፊትም እሱን ለመርዳት ያዶረገውን ሙከራ ሁሉ ታወሰው ። ከራሱ ጋር ተጣልቶ በሰይጣናዊ ግፊት ፎቅ ላይ በቆመበት ጊዜ የደረሰለት ዕለት ትዝ
አለው ። “ እባክህ ችግርህን ንገረኝና ልረዳልህ ብቻህን አትጨነቅ” በማለት አቤልን የወተወተበትም ጊዜ ነበር።
እና አሁን ጥረቱ ፍሬ አስገኘ ።
“ አንብበህ ጨረስክ ? ” አለችው ሞኒካ • ተመልሳ መጥታ ። ዐይኑ ዕንባ አቅርሮ ተመለከተች ። አቤል በትዕግሥት የፍቅር ቃላት ልቡ ተነክቶ የፍቅር ዕንባ ሲያነባ ከአሁን በፊት በእሷ ምክንያት የደረሰበት ቁስል እየሻረለት ነበር ።
አዎ ጨረስኩ ” ኣላት ዝግ ባለ ድምፅ ዐይን ዐይኗን እያየ።
"እንዴት ነው ? ?
ድንቅ ነው ፤ ሸጋ ነው ! ”
እኔም መልስ መጸፍ ይኖርብኛል ” አላት ጸጉሩን እያሻሸ።
እዚሁ ድረስ ትመጣልሃልች ደብዳቤ መጻፍም አያስፈልግህ ” አለችው ሞኒካ ፈገግ እንዳለች ።
"መቼ ?
"እሑድ ጠዋት"።
የያዘውን ቀን አሰበ ።ሐሙስ ነው ለእሑድ ገና ሁለት ቀንና ሦስት ሌሊት ይቀረዋል ። እንዴት ይደርስ ይሆን ?የትዕግሥትን ፎቶግራፍ ከጠረጴዛው ላይ አንሥቶ እንደገና ተመለከተው ።
አቤል በዚህ ሐሳብ ውስጥ በመዋዠቅ ላይ እንዳለ የምሳ ሰዓት ደርሶ ዮናታን መጡ ።ከምሳቸዩ በፊት ወደ ጥናት ክፍሉ ወስዶ ያስተናገዳቸው አቤል ነበር ።
“ ጽሑፉን ” ኮ ጀመርኩት! ” አላቸው ፡ በደስታና በኵራት ድምፅ ።ግሩም ! ” አሉት ዮናታን ፡ ጠረጴዛው ላይ ያሉትን
ቁሳቁሶች እያዩ ። የትዕግሥት ፎቶግራፍ ከመጽሐፉና ከወረቀቶቹ ጐልቶ ታያቸው ። ሊጠይቁት አሰቡና ስሜታቸውን ቆንጠጥ አደረጉ ።አሁንም እንደ ድሮው ይደብቃቸው ይሆን ?
እሷም ልትመጣ ነው ፤ ደብዳቤዋ ደርሶኛል አላቸው : ዐይናቸውን ተከትሉ ስሜታቸው ያረፈበትን በመገመት ።
ግሩም ! ሥራና ፍቅር ተገጣጠሙ በለኛ ! ” አሉት ደስታ ፈንቅሎአቸው ።
ዐይናቸው ከፎቶግራፉ ወደ ጥናት ጽሓፉ ሲሸጋገር ደግሞ ከወረቀቱ አናት ላይ ፡ “ በዚህ ዓለም ላይ ታላቅና ክቡር ፍጡር ሰው ነው የሚለው መንደርደሪያ ደምቆ
ተመለከቱ ።
“ ፍጹም ጤናማ አመለካከት ነው ፤ጤናማ ኅብረተሰብ የጨዋማ ግለሰቦች ውጤት ነው ብለው አሰቡ ።
“በጅማሬህ በጣም ተደስቼአለሁ ። ቀጥልበት ታላቅ ሥራ ሠርተህ ታላቅ ሰው የምትሆንበትን ጊዜ በተስፋ እጠብቃለሁ አሉት ።
ፈገግ እያለ ዐይን ዐይናቸውን ተመለከታቸው ያ መነጽሩን ዐልፎ ዐይናቸው ውስጥ ፍቅር ይነበባል ።
የመጨረሻ ዐረፍተ ነገራቸው ጭንቅላቱ ውስጥ ደወለበት።...
💥ይቀጥላል💥
ይህን ሁሉ የምጽፈው የቆየ ቁስልህን ለመቀስቀስ አይደለም ። በአንድ በኩል ደብዳቤው በእርግጥ ከእኔ ከት ዕግሥት የተላከልህ መሆኑን እንድታምንበት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ስሜትህ ያልገባኝ ወይም ሥቃይህንን ያልተረዳሁልህ እንዳይመስልህ ነው ።
“ከላይ እንደ ገለጽኩልህ፡ችግሩን በመፍራት ፍቅርህን ታግዬ የማሸንፈው አልሆንኩም ። ብሞክረውም አንተን መርሳት ፍጹም የማይቻል ሙከራ ሆነብኝ። ምክንያቱም በአካባቢዬ ሴቶች ስለ አንተ ሲያወሩ በሰማሁ ቁጥር ስሜቴ ይቀሰቀሳል። ስምህን የሚያውቁት፡ “ ያ ጎበዙ ተማሪ” በሚል ቅጽል ነው የሚጠሩህ ። ይህ ቃል በእኔ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ነው ያሳደረብኝ ። በጉብዝናው በሚደነቅ ተማሪ መፈቀር ደስ ያሰኛል። ግን ደግሞ ግንኙነታችን ከዐይን አለ ማለፉን ሳመዛዝን ያበሽቀኛል ። ያ ሁሉ ዐልፎአል ። አሁን ስሜቴን አፍረጥርጨ ያወጣሁልህ ይመስለኛል ። አንተም ግልጽ ሁንልኝ ። ፍቅርን ሕመም ያደረግነው እኛው ነን ፤እባክህ ጐንለጐን ቁጭ ብለን አንተ በእኔ ፥ እኔ ባንተ እንደሰት ። ትምህርትህ በእኔ ምክንያት በመቋረጡ አዝናለሁ ። የምረዳህም
ሆን የምክስህ ነገር ቢኖር፡ ከወዲሁ ሙሉ ፈቃደኝነቴን እገልጽልሃለሁ ። በእኔ ግምት ካሳው ፍቅር ነው ፍቅሬን ሰጥቼህ ፍቅርህን ከመቀበል ሌላ ምን መፍትሔ ይኖራል ?
ያንተው ትዕግሥት አዳነ ”
አቤል ደብዳቤውን ሁለቴ አንብቦ በዝግታ አጠፈው ።እውስጡ ያነበበው የፍቅር ቃላትን ብቻ ሳይሆን እንባም ጭምር ነው ትዕግሥት ፊቷ በእንባ ሳይታጠብ ይህን
ደብዳቤ ጻፈች ማለት ዘበት ነው ። ጽሑፉን ያነበበ ሳይሆን ድምጿን የሰማ መሰለው ። ግን በእርግጥ ትዕግሥት እንዲህ ግልጽ ሆና የውስጧን የምትናገር ሴት ትሆን ? ማነው ጥፋተኛው ? ” የሚለው ቃል ታወሰውና፡ “እውነት ማነው?” ሲል አሰበ ። እሷንም ራሱንም ጥፋተኛ ማድረግ አልቻለም ። አንዲት የፍቅር ቃል እወድሻለሁ ብትለኝ ” ያለችው አንጀቱን በላው ። ነገር ግን ቃሏ አንድ መሆኗ ሳይሆን ክብደቷ ነው ለትዕግሥት ያልገባት ። ይህችን በፍቅረኛ ፊት መተንፈስ መቻል ምንኛ መታደል ነው !
ስለ እስክንድር አሰበ ። ለደብዳቤዉ መጻፍ ያደረገው ጥረት አስገረመው ። ከአሁን በፊትም እሱን ለመርዳት ያዶረገውን ሙከራ ሁሉ ታወሰው ። ከራሱ ጋር ተጣልቶ በሰይጣናዊ ግፊት ፎቅ ላይ በቆመበት ጊዜ የደረሰለት ዕለት ትዝ
አለው ። “ እባክህ ችግርህን ንገረኝና ልረዳልህ ብቻህን አትጨነቅ” በማለት አቤልን የወተወተበትም ጊዜ ነበር።
እና አሁን ጥረቱ ፍሬ አስገኘ ።
“ አንብበህ ጨረስክ ? ” አለችው ሞኒካ • ተመልሳ መጥታ ። ዐይኑ ዕንባ አቅርሮ ተመለከተች ። አቤል በትዕግሥት የፍቅር ቃላት ልቡ ተነክቶ የፍቅር ዕንባ ሲያነባ ከአሁን በፊት በእሷ ምክንያት የደረሰበት ቁስል እየሻረለት ነበር ።
አዎ ጨረስኩ ” ኣላት ዝግ ባለ ድምፅ ዐይን ዐይኗን እያየ።
"እንዴት ነው ? ?
ድንቅ ነው ፤ ሸጋ ነው ! ”
እኔም መልስ መጸፍ ይኖርብኛል ” አላት ጸጉሩን እያሻሸ።
እዚሁ ድረስ ትመጣልሃልች ደብዳቤ መጻፍም አያስፈልግህ ” አለችው ሞኒካ ፈገግ እንዳለች ።
"መቼ ?
"እሑድ ጠዋት"።
የያዘውን ቀን አሰበ ።ሐሙስ ነው ለእሑድ ገና ሁለት ቀንና ሦስት ሌሊት ይቀረዋል ። እንዴት ይደርስ ይሆን ?የትዕግሥትን ፎቶግራፍ ከጠረጴዛው ላይ አንሥቶ እንደገና ተመለከተው ።
አቤል በዚህ ሐሳብ ውስጥ በመዋዠቅ ላይ እንዳለ የምሳ ሰዓት ደርሶ ዮናታን መጡ ።ከምሳቸዩ በፊት ወደ ጥናት ክፍሉ ወስዶ ያስተናገዳቸው አቤል ነበር ።
“ ጽሑፉን ” ኮ ጀመርኩት! ” አላቸው ፡ በደስታና በኵራት ድምፅ ።ግሩም ! ” አሉት ዮናታን ፡ ጠረጴዛው ላይ ያሉትን
ቁሳቁሶች እያዩ ። የትዕግሥት ፎቶግራፍ ከመጽሐፉና ከወረቀቶቹ ጐልቶ ታያቸው ። ሊጠይቁት አሰቡና ስሜታቸውን ቆንጠጥ አደረጉ ።አሁንም እንደ ድሮው ይደብቃቸው ይሆን ?
እሷም ልትመጣ ነው ፤ ደብዳቤዋ ደርሶኛል አላቸው : ዐይናቸውን ተከትሉ ስሜታቸው ያረፈበትን በመገመት ።
ግሩም ! ሥራና ፍቅር ተገጣጠሙ በለኛ ! ” አሉት ደስታ ፈንቅሎአቸው ።
ዐይናቸው ከፎቶግራፉ ወደ ጥናት ጽሓፉ ሲሸጋገር ደግሞ ከወረቀቱ አናት ላይ ፡ “ በዚህ ዓለም ላይ ታላቅና ክቡር ፍጡር ሰው ነው የሚለው መንደርደሪያ ደምቆ
ተመለከቱ ።
“ ፍጹም ጤናማ አመለካከት ነው ፤ጤናማ ኅብረተሰብ የጨዋማ ግለሰቦች ውጤት ነው ብለው አሰቡ ።
“በጅማሬህ በጣም ተደስቼአለሁ ። ቀጥልበት ታላቅ ሥራ ሠርተህ ታላቅ ሰው የምትሆንበትን ጊዜ በተስፋ እጠብቃለሁ አሉት ።
ፈገግ እያለ ዐይን ዐይናቸውን ተመለከታቸው ያ መነጽሩን ዐልፎ ዐይናቸው ውስጥ ፍቅር ይነበባል ።
የመጨረሻ ዐረፍተ ነገራቸው ጭንቅላቱ ውስጥ ደወለበት።...
💥ይቀጥላል💥
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
እነሱ ለትህትና ሕይወት እንደዚያ ሲሯሯጡ ደግሞ የእንደሻው ወላጆች ደግሞ የልጃቸውን ህይወት ለማትረፍ ከላይ ከተች እየተሯሯጡም ብቻ ሳይሆን እየተራወጡ ናቸው። የእንደሻው ጉዳት ከባድ ነበር። በተለይ አንዷ ጥይት የራስ ቅሉን በስታው ስላለፈች፤ የአእምሮ ቀውስ
እንዳያስከትልበት፤ ከፍተኛ ስጋት አለ፡፡
በተፈጠረው አደጋ ምክንያት የእንደሻው ወላጆችና የአዜብ ወላጆችም ግንኙነት አቋርጠዋል፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ...
"ያቺን የተረገመች ልጅ አምጥታ ልጃችንን ልታስገድለው የነበረችው አዜብ ነች በሚል ሲሆን፤ ፀቡን ከአዜብ ጋር ብቻ ሳይሆን ከቤተሰቦቿ ጭምር አድርገውታል :: እነሱ እንደዚያ ብለው ይናገሩ እንጂ ፤ የአዜብ ወላጆች ሁኔታው ሊፈጠር የቻለው አለሌው ልጃቸው
በፈፀመው ተደጋጋሚ አስነዋሪ ድርጊት ሳቢያ መሆኑን ሲያውቁ የክርስትና ልጃችን ነው በሚል ምክንያት ብቻ ፤ በትህትና ላይ ሊፈርዱባት
አልደፈሩም....
"ሁሉንም ስራው ያውጣው በማለት መጨረሻውን ለማየት እየተጠባበቁ ናቸው፡፡ ትህትና ጤናዋ በከፍተኛ ፍጥነት እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም፤ ጐን ለጐን በነፍስ ማጥፋት ሙከራ ወንጀል በአቃቤ ህግ ክስ ተመሰረተባት፡፡ አዜብና ብሩክ ይህንን እንዳወቁ ቀጣዩ ትኩረታቸው
በምን ላይ መሆን እንዳለበት በስፋት ተመካከሩ፡፡ ከዚያም አንዳንድ
በመከላከያነት ይጠቅማሉ ያሏቸውን ማስረጃዎች ለማሰባሰብ ፤ ሁለቱም
በየፊናቸው ሩጫ ጀመሩ፡፡ ለዚህ ጉዳይ አበራ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገመቱ :: ምክንያቱም አበራ በእንደሻው ክህደት የደረሰበትና፤ በትህትና ላይ ስለተፈፀመው ወንጀል በሚገባ የሚያውቅ የአይን ምስክር ስለነበረ ነው፡፡ አበራ በእንደሻው ስለተፈፀመበት ክህደት ለአገሩ ሁሉ ሲያወራ ለአዜብም አጫውቷት ነበር ፡፡
ከዝምድና ይልቅ ገንዘብን አስበልጦ አስር
አመት ሙሉ ያጠራቀምኩትን ገንዘቤን ወስዶ ከከበረበት በኋላ ከዳኝ፡፡ በጋራ
እናድግበታለን ብሎ የገባውን ቃሉን አፍርሶ አባረረኝ " በማለት በምሬት ነበር የገለፀላት፡፡ ታዲያ ያ ሁሉ በደል የተፈፀመበት ሰው ፍርድ ቤት ቀርቦ እውነቱንና የሚያውቀውን ከመናገር ወደኋላ ሊል ይችላል? ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡ በፍፁም ወደኋላ አይልም ስትል ተማመነች፡፡ምክንያቱም እሱ እንደዚያ በንዴት እየተንቀጠቀጠ
ሲነግራት...
“አይዞህ አበራ ተወው፡፡ አንተ ጤና ሁን እንጂ ፤ገንዘብ አላፊ ጠፊ ነው፡፡ በክህደት የተገኘ ገንዘብ ደግሞ የትም አያደርስም፡፡
ከሰራህ ከካደህ ሰው በላይ መሆን ትችላለህ :: አይዞህ! እግዚአብሄር ላንተ ያለውን ምንግዜም አታጣውም " በማለት ትልቅ የማፅነኛ ቃል ለግሳው ነበር፡፡ ያንን
የሰጠችውን የተስፋ ቃል እንኳ አስታውሶ እሺ ይላት ይሆን? ወይንስ እሱም እንደወላጆቹ ተደርቦ ከእውነት ጀርባ ይቆም ይሆን? ልቧ ተጠራጠረ፡፡ ለማንኛውም አለችና ስልክ ደወለችለት :: ስልኩን አነሳና እሷ መሆንዋን ሲያውቅ የሞቀ ሰላምታ አቀረበላት፡፡ ትንሽ እፎይ አለች በልቧ፡፡ለጉዳይ እንደምትፈልገው
ስትገልፅለት፤ በደስታ ተቀብሎ የሚገናኙበትን ቦታ ተቀጣጥረው
ተሰነባበቱ፡፡ በማግስቱ በቀጠሮው ቦታ ቀድሞ የደረሰው እሱ ነበር።
የተፈለገበትን ጉዳይ ስትነግረው...
"ተይ እንጂ አዜብ እቤት ድረስ የወሰድኳት እኮ እኔ ነኝ፡፡በወንጀለኛነት አያስጠይቅህም ነው የምትይኝ?" ሲል በጥርጣሬ ጠየቃት።
"ስለሱ ከሻምበል ጋር በደንብ ተነጋግረንበታል፡፡ አንተን በወንጀል
ተባባሪነት እንዳያስጠይቅህ በቂ ምክንያት ማቅረብ ይቻላል፡፡”
"ለምሳሌ ምን?"
"አበራ ሙት ምንም አትፍራ! በዚህ ጉዳይ አንተ በጥፋተኛነት እንድትጠየቅ የሚፈልግ ሰው የለም፡፡ አንድ ማወቅ ያለብህ ነገር ፧ አንተ ይዘሃት የሄድከው ወደ ቀጣሪዋ ቤት እንጂ፤ ወንጀል
ወደሚፈጸምበት ጫካ ውስጥ አይደለም፡ቀጣሪዋ ቤት አደረስካት ማለት፤ እንደሻው ደብድቦና፤ አስገድዶ፧ ክብረ ንፅህናዋን እንዲደፍራት አደረክ ማለት አይደለም :: የቀጣሪዋን ቤት የወንጀል መፈፀሚያ ዋሻ ያደረገው ወንጀለኛ ብቻ ነው ለዚህ ተጠያቂ የሚሆነው፡፡ አይዞህ ምንም የሚያስፈራ ነገር የለውም፡ አበራን ለማሳመን ብሎ ብሩክ ያስጠናትን ደሰኮረችለት፡፡ አበራ ልቡ ትንሽ ተለሳለሰ፡፡
"በሌላ በኩል ብታየው ደግሞ የቀጣሪዋ ባለቤት ልጅ የቅጥር ውል እንድትፈርም ይዘሃት ና ብሎ አዘዘህ :: አንተም ይህን ነገርካት። እሷም እሺ ብላ ሳታስገድዳት በፈቃደኝነት አብራህ ሄደች። ከዚያም አንተ በሌለህበት እንደሻው ወንጀል ፈፅሞባት ደረስክ፡፡ በቃ፡፡ ይህ አይደለም
ታሪኩ? አንተን የሚያስጠይቅህ ምኑ ነው ታዲያ?" ስትል የማደፋፈሪያ
ሀሳብ አዥጐደጐደችለት፡፡
በልቡ ያሳደረው ጥርጣሬ ሙሉ ለሙሉ ባይጠፋለትም፤ በአዜብ አቀራረብ ተስማማ፡፡ እንዳለችውም እሱን በቀጥታ ተጠያቂ ሊያደርገው የሚችል ጭብጥ እንደሌለ ተሰማው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ
ያቺ ምስኪን እንጀራ ፈላጊ ልጅ ፤ በደም ተጨማልቃ ወድቃ ያያት እለት የተሰማው ስሜት ፊቱ ላይ ድቅን አለበት፡፡ በተፈፀመባት ወንጀል ከልቡ አዝኖ ነበር፡፡ በዚህ ላይ ያ ግፈኛ ከሃዲ ከሱቁ ካባረረው በኋላ አሁን አሁን በርካታ ካፒታል በማንቀሳቀስ በቅናት እያቃጠለው
ነው፡፡ በጥይት መቃጠሉን የሰማ እለት " እሰይ የእጁን ነው ያገኘው"ነበር ያለው፡፡ አሁን ደግሞ እሱ ተጠያቂ በማይሆንበት ሁኔታ ለምን ያየውን ከመመስከር ወደ ኋላ ማለት እንደሌለበት ተገነዘበ ፡፡ያየኽውን እውነት መሰከርክ ብሎ የሚፈርድበት ዘመድ እንደማይኖርና፤ ቢኖርም መፅሀፍ ቅዱስ ይዞ በሚፈፅመው መሃላ በውሸት መስክሮ ነፍሱን ማስኮነን እንደሌለበት ተሰማው። እንደሻውን ሊበቀል
የሚችልበትን ይህንን መልካም አጋጣሚ ሊጠቀምበት ወሰነ : እንቢ ቢልስ የት ሊደርስ ? በተለይ አዜብ እየነገረችው
ያለው ፣ ባለስልጣን ፖሊስ ከአዜብ በስተጀርባ መኖሩን ነው፡፡ በተለይ "ሻምበል ጋር በደንብ ተነጋግረንበታል"
ስትለው ምን እያለች እንደሆነ
ገብቶታል፡፡አልመሰክርም ቢል በተባባሪ ወንጀለኛነት ተፈርጆ፣ ለፍርድ እንደሚቀርብ እየነገረችው ነው፡፡ ይሄንን ጭምር አስቦ፤ ልቡ ስለፈራ፤ ያየውን ሁሉ በዝርዝር ሊያስረዳና፤ ለትህትና ድንበሩ የመከላከያ ምስክር ሊሆን ቃል ገባላት፡፡ ቃል መግባት ብቻም ሳይሆን ተጨማሪ ማስረጃ ጠቆማት..
"እኔ ብቻ ሳልሆን በዚያን እለት ሁኔታውን የተመለከተችው የቤት ሰራተኛዋ ወርቅ ያንጥፉም ያየችውን ሁሉ እውነቱን ሳትደብቅ እንድትመሰክር እናደርጋለን :: ደግሞም ትመሰክራለች፡፡ አትጠራጠሪ!
በትህትና ሁኔታ በጣም ነው ያዘነችው፡፡እሷም ስመ እግዚአብሄርን ጠርታ
ያየችውን ሁሉ ትመሰክራለች፡፡ አይዞሽ ! " አላት፡፡ አዜብ ከጠበቀችው በላይ ተባባሪ ሆኖ ስለኣገኘችው፤ በደስታ እቅፍ አደረገችው፡፡ በዚሁ መሰረት አበራና ወርቅ ያንጥፉ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው፤ የምስክርነት ቃላቸውን እንዲሰጡ ተደረገ፡፡ ቀኑን፡ ሰአቱን፡ የድርጊቱን አፈፃፀም፡ ዝርዝር ሁኔታውን፤ በሙሉ በአንድ አይነትና ፤ ተመሳሳይ በሆነ ቃል
መሰከሩ። ያም ብቻ ሳይሆን አንዱአለምን ጋርጠው በሚል ቅፅል ስሙ በሚታወቀው ወሮበላ እንዳይሞት፤ እንዳይድን፤ አደርጐ ያስደበደበው
መሆኑን፤ ራሱ እንደሻው በኩራት ሲናገር መስማቱን፧ ጭምር ገለፀ፡፡
በእርግጥም እንደሻው ያንን ለአበራ የተናገረው፤ ይሄ ይመጣብኛል ብሎ ሳይሆን፤ አንተም አርፈህ የማትቀመጥና ወሬ አበዛለሁ የምትል ከሆነ፤ አስወቅጥሀለሁ፤ የሚል ማስጠንቀቂያ ለመስጠት ነበር፡፡ ሆኖም በዚህ አጋጣሚ እንደሻውን የደበደበው ጉልበተኛ
ስለታወቀ፤ ወዲያውኑ ታድኖ እንዲያዝ ሲደረግ ፤ አበራ ማንነቱን በማሳየትና የሚገኝበትን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
እነሱ ለትህትና ሕይወት እንደዚያ ሲሯሯጡ ደግሞ የእንደሻው ወላጆች ደግሞ የልጃቸውን ህይወት ለማትረፍ ከላይ ከተች እየተሯሯጡም ብቻ ሳይሆን እየተራወጡ ናቸው። የእንደሻው ጉዳት ከባድ ነበር። በተለይ አንዷ ጥይት የራስ ቅሉን በስታው ስላለፈች፤ የአእምሮ ቀውስ
እንዳያስከትልበት፤ ከፍተኛ ስጋት አለ፡፡
በተፈጠረው አደጋ ምክንያት የእንደሻው ወላጆችና የአዜብ ወላጆችም ግንኙነት አቋርጠዋል፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ...
"ያቺን የተረገመች ልጅ አምጥታ ልጃችንን ልታስገድለው የነበረችው አዜብ ነች በሚል ሲሆን፤ ፀቡን ከአዜብ ጋር ብቻ ሳይሆን ከቤተሰቦቿ ጭምር አድርገውታል :: እነሱ እንደዚያ ብለው ይናገሩ እንጂ ፤ የአዜብ ወላጆች ሁኔታው ሊፈጠር የቻለው አለሌው ልጃቸው
በፈፀመው ተደጋጋሚ አስነዋሪ ድርጊት ሳቢያ መሆኑን ሲያውቁ የክርስትና ልጃችን ነው በሚል ምክንያት ብቻ ፤ በትህትና ላይ ሊፈርዱባት
አልደፈሩም....
"ሁሉንም ስራው ያውጣው በማለት መጨረሻውን ለማየት እየተጠባበቁ ናቸው፡፡ ትህትና ጤናዋ በከፍተኛ ፍጥነት እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም፤ ጐን ለጐን በነፍስ ማጥፋት ሙከራ ወንጀል በአቃቤ ህግ ክስ ተመሰረተባት፡፡ አዜብና ብሩክ ይህንን እንዳወቁ ቀጣዩ ትኩረታቸው
በምን ላይ መሆን እንዳለበት በስፋት ተመካከሩ፡፡ ከዚያም አንዳንድ
በመከላከያነት ይጠቅማሉ ያሏቸውን ማስረጃዎች ለማሰባሰብ ፤ ሁለቱም
በየፊናቸው ሩጫ ጀመሩ፡፡ ለዚህ ጉዳይ አበራ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገመቱ :: ምክንያቱም አበራ በእንደሻው ክህደት የደረሰበትና፤ በትህትና ላይ ስለተፈፀመው ወንጀል በሚገባ የሚያውቅ የአይን ምስክር ስለነበረ ነው፡፡ አበራ በእንደሻው ስለተፈፀመበት ክህደት ለአገሩ ሁሉ ሲያወራ ለአዜብም አጫውቷት ነበር ፡፡
ከዝምድና ይልቅ ገንዘብን አስበልጦ አስር
አመት ሙሉ ያጠራቀምኩትን ገንዘቤን ወስዶ ከከበረበት በኋላ ከዳኝ፡፡ በጋራ
እናድግበታለን ብሎ የገባውን ቃሉን አፍርሶ አባረረኝ " በማለት በምሬት ነበር የገለፀላት፡፡ ታዲያ ያ ሁሉ በደል የተፈፀመበት ሰው ፍርድ ቤት ቀርቦ እውነቱንና የሚያውቀውን ከመናገር ወደኋላ ሊል ይችላል? ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡ በፍፁም ወደኋላ አይልም ስትል ተማመነች፡፡ምክንያቱም እሱ እንደዚያ በንዴት እየተንቀጠቀጠ
ሲነግራት...
“አይዞህ አበራ ተወው፡፡ አንተ ጤና ሁን እንጂ ፤ገንዘብ አላፊ ጠፊ ነው፡፡ በክህደት የተገኘ ገንዘብ ደግሞ የትም አያደርስም፡፡
ከሰራህ ከካደህ ሰው በላይ መሆን ትችላለህ :: አይዞህ! እግዚአብሄር ላንተ ያለውን ምንግዜም አታጣውም " በማለት ትልቅ የማፅነኛ ቃል ለግሳው ነበር፡፡ ያንን
የሰጠችውን የተስፋ ቃል እንኳ አስታውሶ እሺ ይላት ይሆን? ወይንስ እሱም እንደወላጆቹ ተደርቦ ከእውነት ጀርባ ይቆም ይሆን? ልቧ ተጠራጠረ፡፡ ለማንኛውም አለችና ስልክ ደወለችለት :: ስልኩን አነሳና እሷ መሆንዋን ሲያውቅ የሞቀ ሰላምታ አቀረበላት፡፡ ትንሽ እፎይ አለች በልቧ፡፡ለጉዳይ እንደምትፈልገው
ስትገልፅለት፤ በደስታ ተቀብሎ የሚገናኙበትን ቦታ ተቀጣጥረው
ተሰነባበቱ፡፡ በማግስቱ በቀጠሮው ቦታ ቀድሞ የደረሰው እሱ ነበር።
የተፈለገበትን ጉዳይ ስትነግረው...
"ተይ እንጂ አዜብ እቤት ድረስ የወሰድኳት እኮ እኔ ነኝ፡፡በወንጀለኛነት አያስጠይቅህም ነው የምትይኝ?" ሲል በጥርጣሬ ጠየቃት።
"ስለሱ ከሻምበል ጋር በደንብ ተነጋግረንበታል፡፡ አንተን በወንጀል
ተባባሪነት እንዳያስጠይቅህ በቂ ምክንያት ማቅረብ ይቻላል፡፡”
"ለምሳሌ ምን?"
"አበራ ሙት ምንም አትፍራ! በዚህ ጉዳይ አንተ በጥፋተኛነት እንድትጠየቅ የሚፈልግ ሰው የለም፡፡ አንድ ማወቅ ያለብህ ነገር ፧ አንተ ይዘሃት የሄድከው ወደ ቀጣሪዋ ቤት እንጂ፤ ወንጀል
ወደሚፈጸምበት ጫካ ውስጥ አይደለም፡ቀጣሪዋ ቤት አደረስካት ማለት፤ እንደሻው ደብድቦና፤ አስገድዶ፧ ክብረ ንፅህናዋን እንዲደፍራት አደረክ ማለት አይደለም :: የቀጣሪዋን ቤት የወንጀል መፈፀሚያ ዋሻ ያደረገው ወንጀለኛ ብቻ ነው ለዚህ ተጠያቂ የሚሆነው፡፡ አይዞህ ምንም የሚያስፈራ ነገር የለውም፡ አበራን ለማሳመን ብሎ ብሩክ ያስጠናትን ደሰኮረችለት፡፡ አበራ ልቡ ትንሽ ተለሳለሰ፡፡
"በሌላ በኩል ብታየው ደግሞ የቀጣሪዋ ባለቤት ልጅ የቅጥር ውል እንድትፈርም ይዘሃት ና ብሎ አዘዘህ :: አንተም ይህን ነገርካት። እሷም እሺ ብላ ሳታስገድዳት በፈቃደኝነት አብራህ ሄደች። ከዚያም አንተ በሌለህበት እንደሻው ወንጀል ፈፅሞባት ደረስክ፡፡ በቃ፡፡ ይህ አይደለም
ታሪኩ? አንተን የሚያስጠይቅህ ምኑ ነው ታዲያ?" ስትል የማደፋፈሪያ
ሀሳብ አዥጐደጐደችለት፡፡
በልቡ ያሳደረው ጥርጣሬ ሙሉ ለሙሉ ባይጠፋለትም፤ በአዜብ አቀራረብ ተስማማ፡፡ እንዳለችውም እሱን በቀጥታ ተጠያቂ ሊያደርገው የሚችል ጭብጥ እንደሌለ ተሰማው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ
ያቺ ምስኪን እንጀራ ፈላጊ ልጅ ፤ በደም ተጨማልቃ ወድቃ ያያት እለት የተሰማው ስሜት ፊቱ ላይ ድቅን አለበት፡፡ በተፈፀመባት ወንጀል ከልቡ አዝኖ ነበር፡፡ በዚህ ላይ ያ ግፈኛ ከሃዲ ከሱቁ ካባረረው በኋላ አሁን አሁን በርካታ ካፒታል በማንቀሳቀስ በቅናት እያቃጠለው
ነው፡፡ በጥይት መቃጠሉን የሰማ እለት " እሰይ የእጁን ነው ያገኘው"ነበር ያለው፡፡ አሁን ደግሞ እሱ ተጠያቂ በማይሆንበት ሁኔታ ለምን ያየውን ከመመስከር ወደ ኋላ ማለት እንደሌለበት ተገነዘበ ፡፡ያየኽውን እውነት መሰከርክ ብሎ የሚፈርድበት ዘመድ እንደማይኖርና፤ ቢኖርም መፅሀፍ ቅዱስ ይዞ በሚፈፅመው መሃላ በውሸት መስክሮ ነፍሱን ማስኮነን እንደሌለበት ተሰማው። እንደሻውን ሊበቀል
የሚችልበትን ይህንን መልካም አጋጣሚ ሊጠቀምበት ወሰነ : እንቢ ቢልስ የት ሊደርስ ? በተለይ አዜብ እየነገረችው
ያለው ፣ ባለስልጣን ፖሊስ ከአዜብ በስተጀርባ መኖሩን ነው፡፡ በተለይ "ሻምበል ጋር በደንብ ተነጋግረንበታል"
ስትለው ምን እያለች እንደሆነ
ገብቶታል፡፡አልመሰክርም ቢል በተባባሪ ወንጀለኛነት ተፈርጆ፣ ለፍርድ እንደሚቀርብ እየነገረችው ነው፡፡ ይሄንን ጭምር አስቦ፤ ልቡ ስለፈራ፤ ያየውን ሁሉ በዝርዝር ሊያስረዳና፤ ለትህትና ድንበሩ የመከላከያ ምስክር ሊሆን ቃል ገባላት፡፡ ቃል መግባት ብቻም ሳይሆን ተጨማሪ ማስረጃ ጠቆማት..
"እኔ ብቻ ሳልሆን በዚያን እለት ሁኔታውን የተመለከተችው የቤት ሰራተኛዋ ወርቅ ያንጥፉም ያየችውን ሁሉ እውነቱን ሳትደብቅ እንድትመሰክር እናደርጋለን :: ደግሞም ትመሰክራለች፡፡ አትጠራጠሪ!
በትህትና ሁኔታ በጣም ነው ያዘነችው፡፡እሷም ስመ እግዚአብሄርን ጠርታ
ያየችውን ሁሉ ትመሰክራለች፡፡ አይዞሽ ! " አላት፡፡ አዜብ ከጠበቀችው በላይ ተባባሪ ሆኖ ስለኣገኘችው፤ በደስታ እቅፍ አደረገችው፡፡ በዚሁ መሰረት አበራና ወርቅ ያንጥፉ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው፤ የምስክርነት ቃላቸውን እንዲሰጡ ተደረገ፡፡ ቀኑን፡ ሰአቱን፡ የድርጊቱን አፈፃፀም፡ ዝርዝር ሁኔታውን፤ በሙሉ በአንድ አይነትና ፤ ተመሳሳይ በሆነ ቃል
መሰከሩ። ያም ብቻ ሳይሆን አንዱአለምን ጋርጠው በሚል ቅፅል ስሙ በሚታወቀው ወሮበላ እንዳይሞት፤ እንዳይድን፤ አደርጐ ያስደበደበው
መሆኑን፤ ራሱ እንደሻው በኩራት ሲናገር መስማቱን፧ ጭምር ገለፀ፡፡
በእርግጥም እንደሻው ያንን ለአበራ የተናገረው፤ ይሄ ይመጣብኛል ብሎ ሳይሆን፤ አንተም አርፈህ የማትቀመጥና ወሬ አበዛለሁ የምትል ከሆነ፤ አስወቅጥሀለሁ፤ የሚል ማስጠንቀቂያ ለመስጠት ነበር፡፡ ሆኖም በዚህ አጋጣሚ እንደሻውን የደበደበው ጉልበተኛ
ስለታወቀ፤ ወዲያውኑ ታድኖ እንዲያዝ ሲደረግ ፤ አበራ ማንነቱን በማሳየትና የሚገኝበትን
👍2❤1