አትሮኖስ
286K subscribers
121 photos
3 videos
41 files
571 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
መኮትኮት ያለበት ። እናም ኋላቀር አስተሳሰብ ከፈጠረብን ችግር ለመላቀቅ የሁላችንም ጥሪ የሚያተኩረው።
የባህል አብዮት ላይ ነው።

ስብሰባው እንዳለቀ ዮናታን የቸኮሉት ይህን መልካም ዜና ለሚስታቸው ለማብሠር ነበር ። ስብሰባው በጥሩ ሁኔታ
ማለቁ ብቻ ሳይሆን ፥ ከስብሰባው ውጭ በዮናታን ጥረት የተደነቁ ሰዎች አቤልን ለመርዳት ያላቸውን በጎ ፈቃድ ሲገልጹላቸው ደስታቸው ገደብ አጣ ። የአቤልን የትምህርት ጉብዝና ያውቁ የነበሩ ሰዎች፡አቤል ዮናታን ቤት መሆኑ ከተገለጸላቸው በኋላ ትምህርቱን እንደገና እስኪጀምር ድረስ እንደ የዐቅማቸው ገንዘብ በማዋጣት እንደሚተባበሯቸው ነው- የነገሩዋቸው ።

“ ይኸኛውን ርምጃችንን በጥሩ ሁኔታ ተወጥተነዋል ” አሉት ዮናታን እስክንድርን “ የሚቀጥለው ጉዳይ
አቤልን ከትዕግሥት ጋር ማገናኘቱ ወይም ማለያየቱ ነው "
አንድም በጥሩ መንፈስ ልቡ ውስጥ እንድትታሰብ ማድረግ ካልሆነም ከልቡ ውስጥ ፈንቅሎ ማውጣት ! ”

እስክንድር ራሱ ይህን ጉዳይ እያሰበበት ነበር " ስብሰባው እንዳለቀ ፡ ዮናታን ሁኔታውን ለሚስታቸው ለማብሰር ስሜታቸው ሲቻኮል • የእሱ ስሜት ደግሞ ዘሎ ያረፈው ትዕግሥት ላይ ነበር ።አፍ አውጥታ ስለአቤል ከጠየቀችው
ጊዜ ጀምሮ እኒህ የዐይን ፍቅረኞች የሚቀራረቡት የተስፋ ጭላንጭል በልቡ ውስጥ እየፈነጠቀ ነበር ። እናም ለትዕግሥት ስለ አቤል ለማጫወት ወይም እሷ ስለ አቤል ያላትን ጥልቅ ስሜት ለመስማት አጋጣሚ ነበር የሚጠብቀው "

“ አቤልና ትዕግሥትን ማገናኘት ነው እንጂ' ማለያየቱ ምን ሲደረግ ይታሰባል ? ” አላቸው እስክንድር ፈገግ ብሎ
“ ለሕይወቱ እንቅፋት ከሆነችበት አራርቆ እንዲረሳት ማድረጉ ይመረጣል ብዬ ነዋ ! ” አሉ ዮናታን ግራ በተጋባ ስሜት "

እዬዬ ! ልቡ ውስጥ ገብታ ካደገች በኋላ መፈንቀሉ አስቸጋሪ ነው። ለጊዜው ርቆአት ሊረሳት ቢሞክርም ወደ ዩኒቨርስቲ በሚመለስበት ጊዜ ሲያያት ቁስሉ የሚቀሰቀስበት ይመስለኛል ። የአፍላ ፍቅርን ዛፍ ሥሩ መቁረጥ የሚቻል አይመስለኝም " ታዲያ ምን ይሻላል ? ” አሉት ዮናታን በተጨነቀ
ስሜት ።ሁለቱን አገናኝተን የ ፍቅራቸው ከዐይን ተሻግሮ በቅርብ እንዲተሳሰሩ ማድረግ ነዋ ! ”
• ከተቻለማ ጥሩውም መንገድ እሱ ነበር
“አይጠራጠሩ ! ” ሲላቸው ፡ የተማመነበት ነገር ምን አንደሆነ ለራሱም በደንብ ግልጽ ሆኖ አልታወቀውም ነበር ።

💥ይቀጥላል💥
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሰላሳ_ሁለት


#ድርሰት_በትክክል_ገና


እቅዳቸው በአሳዛኝ ሁኔታ መክሸፉን፤ መክሸፍ ብቻም ሳይሆን የሷና የሻምበል ብሩክ ፍቅር እስከ ወዲያኛው ዳግም ላይጠገን እንክትክት ብሎ መሰባበሩን ስትሰማ አዜብ ክፉኛ ደነገጠች፡፡ ምን
የማይሆን ምክር መክሬ ጉድ ያደረኳት፤ በሚል ጸጸት ተቃጠለች፡፡ ለዚህ
ችግር መንስኤው እሷ እንደሆነች
ሁሉ “እኔ ነኝ ጉድ ያደረኩሽ ትሁትዬ፡፡ እኔ ነኝ ጥፋተኛዋ፡፡ ድሮውንም ቢሆን አንቺ አይሆንም ብላሽ ነበር። አጉል የማይሆን ምክር መክሬ እዚህ ጣጣ ውስጥ የከተትኩሽ እኔ ነኝ፡፡በደሉ የኔ ነው፡፡ ወይኔ ጓደኛዬ... እዬዬ እያለች አብራት
ስታለቅስ ዋለች፡፡

እየዋለ እያደረ ግን ለትህትና ህይወት መበላሽት ዋናው ምክንያት እሷ ያለመሆንዋን፤ ትህትና ለተደጋጋሚ ፈተና የተጋለጠችው በሷ ምክንያት ሳይሆን በሌላ ሰው ጦስ መሆኑን፤እያመነች መጣች፡፡የወንጀል ድርጊቱ እንደተፈፀመባት ወዲያውኑ ህጋዊ እርምጃ ማስወሰድ ሲችሉ፤ እንደሻው የአዜብ ወላጆች የክርስትና ልጅ ነው፤ አባቱም ለትህትና ባለውለታ ናቸው፤ በሚል ሰበብ ጉዳዩን አዳፍነው፤ አለባብሰው ማለፋቸው ተገቢ ያለመሆኑ እየተገለጠላት መጣ፡፡ በዚያን ሰአት በደም ተጨማልቃ የጠበቀቻት ትህትና ታየቻት፡፡ ከዚያም ከዶክተር ባይከዳኝና
አሁን ደግሞ ከሻምበል ብሩክ ጋር ለነበራት ግንኙነት ዋናው የጸቡ
መንስኤ የእንደሻው ጦስ መሆኑ ያለጥርጥር ታወቃት፡፡ እንደሻው በሰላም
እንቅልፉን ይለጥጣል፡፡ ትህትና ግን በየቀኑ ታነባለች፡፡ በዚህ ላይ አንድም
ቀን እንኳን የጥፋተኝነት ስሜት ተሰምቶት ይቅርታ ጠይቆ አያውቅም፡፡ስለዚህ የእጁን ማግኘት አለበት ብላ ወሰነች፡፡ በእንደሻው ምክንያት ትህትና ክብረ ንጽህናዋን፣ ሥራዋን፤ እጮኛዋን፤ አጥታለች። ግዴለም! ስትል በልቧ ዛተች፡፡

አንዱ አለም በሁኔታው ግራ ተጋብቶ.. “እታለም ሥራውን ተውሽው እንዴ?” ብሎ የጠየቃት እለት “ትንሽ ዕረፍት ወስጄ ነው
አልተውኩትም” ብላ ዋሽታው ነበር፡፡ በኋላ ግን በውሸቷ መቀጠል አልቻለችም፡፡ ሥራው ያልተስማማት በመሆኑ ያቋረጠችው መሆኑን
ገለፀችለት፡፡
“አይዞሽ ቆንጆ የቢሮ ሥራ ነው የምትይዥው፡፡ የምን ጫማ
መሸጥ ነው”? ሲል ሞራል ሰጣት፡፡
ከሥራው የበለጠ እንዱዓለምን ያሳሰበው እህቱ ይሄንን ሰሞን ሙሉ ለሙሉ መለወጧን፣ በሆነ ባልሆነ ማልቀስ ማብዛቷን፣ ሲጠሯት ቶሎ ያለመስማቷን፣ ፍዝዝ ማለቷን፣ እህል እምብዛም ያለመድፈሯን፣ እንዳትሞት ያህል ብቻ አፏ ላይ ጣል , አድርጋ በቃኝ ማለትን
ማዘውተሯን፣ ሰውነቷ እየጠወለገ መሄዱን፣ በአጠቃላይ ሻምበል ብሩክን
ካገኘች በኋላ ደስተኛ መሆን የጀመረችው ልጅ ሰሞኑን በሚገርም ሁኔታ ሙሉ ለሙሉ ተለውጣ በማስተዋሉ ነው፡፡

በዚህ ላይ ደግሞ እንደታላቅ ወንድሙ የሚያየው “አንዱዓለም እስቲ እንካ ይህችን ለደብተር መግዣ፣ ለፀጉርህ መስተካከያ አይዞህ በርትተህ ተማር” እያለ የሚንከባከበው የእህቱ እኛ የሻምበል ብሩክ ድምፁ እየጠፋ ነው፡፡ ነገሩ አሳሰበው፡፡ አጠራጠረው፡፡
ይሄ ሁኔታ ከሳምንት በላይ አስቆጠረ፡፡ አንዱዓለም ጥርጣሬው እየጨመረ መጣ፡፡ እህቱ ምንም ነገር ልትነግረው ፈቃደኛ አልሆነችም፡፡ መላው ቢጠፋው አዜብን ሊያማክራት ፈለገ፡፡
አዜብ አንጀቷ እየተቃጠለ፤ የዚህ ሁሉ በደል ምንጭ የሆነው እንደሻው የሚቀጣበት መንገድ ጨንቋት ውስጥ ውስጡን በንዴት ስትንጨረጨር ነው የከረመችው፡፡
አንዱዓለም ስለእህቱ ሁኔታ ሲጠይቃት፤ ተደስታ አንድም ሳታስቀር እንደሻው የፈፀመባትን ወንጀል ዘከዘከችለት፡፡ በእህቱ ላይ የተፈፀመውን ወንጀል ሲሰማ አንዱአለም በንዴት ተንዘፈዘፈ። ከዚያም
በላይ እንደ እብድ አድርጎት ነበር፡፡ ከዚያም ያንን ግፈኛ ሊበቀለው
የሚገኝበትን ቦታ ጠየቃት፡፡
አዜብ አላመነታችም፡፡ “አሳይሀለሁ” አለችው፡፡ ለዚሁ ጉዳይ ተቀጣጠሩና፤ እንደሻው የሚገኝበትን ሱቅ ልታሳየው ይዛው ሄደች፡፡
ትህትና ይህንን ሁሉ አታውቅም፡፡ ወንድሟ ከሰው ጋር ተጣልቶ አደጋ እንዳይደርስበት ስለምትሰጋ፤ በፍፁም እንዳይሰማ አዜብን አደራ ብላት ነበር፡፡ አዜብ ግን እሺ አልነግረውም ብትላትም፤ እሱ ቀድሞ ባይጠይቃት ኖሮ ቀድማ ልትነግረው ተዘጋጅታ ነበር፡፡
በሷ እምነት እንደሻው ለፈፀመው ግፍ ተጠያቂ መሆን አለበት፡፡ ለወንጀሉ በቂ ቅጣቱን ማግኘት አለበት፡፡ አለበለዚያም በአፏ አላወጣችውም እንጂ ፤ በሱ ምክንያት ከባድ ችግር ላይ የወደቀች ልጅ
በመሆኗና ክብረ ንጽህናዋን የደፈረው እሱ በመሆኑ ወደደም ጠላም
ሊያገባት ይገባል ነው እምነቷ፡፡
የዚያን ዕለት አንዱዓለም እንቅልፍ በዐይኑ ሳይዞርለት ነጋ:: አንጅቱ እያረረ አደረና፤ በማግስቱ ከቀኑ አሥር ሰዓት ተኩል ሲሆን ብቻውን ወደዚያ ሱቅ ሄደ፡፡
ከሱቁ ሲደርስ እንደሻው ሲጃራውን እያቦነነ አገኘው፡፡ ለመጨረሻ ጊዜ ሲጃራውን ምጉ ቁራጩን በእግሩ ደፈጠጠና የመጣለትን ቁርስ ሊበላ
ሻይ በመቅዳት ላይ እንዳለ፤ ዐይኖቹ እንደ በርበሬ ቀልተው፤ ፊቱ ሳምባ እንደመሰለ፤ በንዴት መላ ሰውነቱ የሚንቀጠቀጥ ወጣት በሩ ላይ ገጭ አለበት፡፡
አንዱአለም የሰራ አካላቱን እንደ ኤሌክትሪክ የሚነዝር የጥላቻ
ስሜት ወሮት ተንደርድሮ ሄደና ያንን የሻይ ማንቆርቆሪያ አንስቶ ፊቱ ላይ ቸለሰበት፡፡ እንደሻው በዚያ ትኩሳ ሻይ ተቀቀለ፡፡ በድንጋጤ ከባንኮኒው ላይ ዘሎ ወጣና ግብ ግብ ተያያዙ፡፡

አንዱዓለም በእህልና፤ በቁጭት፤ ሰይጣናዊ ጉልበት ተላብሷል፡፡
እንደሻው ግን በብርክ ስለተዋጠ ሊቋቋመው አልቻለም፡፡ እየደጋገመ ፊቱን
እንደተርብ ጠዘጠዘው፡፡ ከዚያም ትንሽ በትንሹ ከድንጋጤው ተመልሶ
አንዱዓለምን ሊያንቀው ሲዘጋጅ ጐረቤትም መንገደኛም መሀል ገባና
ገላገላቸው፡፡
አንዱዓለም እየጮኸ ያዙኝ ልቀቁኝ እያለ ይሳደብ ጀመር፡፡
“አንተ የውሻ ልጅ!! በዚህ ብቻ የምለቅህ እንዳይመስልህ...!”
አለው፡፡ እንደሻው እየተርበተበተና በድንጋጤ ዐይኖቹ እንደተበለጠው
ይህንን ሰይጣን ማን ላከብኝ በሚል ስሜት ግራ ተጋብቶ ይመለከተዋል፡፡
አበራ በሃሣቡ ድቅን አለ፡፡ “በቃ አበራ የላከው ሰው መሆን አለበት” አለ በልቡ፡፡

መቼም አንዳንድ ግዜ ፍቅር እንደ አጀማመሩ አያልቅም፡፡
በተለይ በጥቅም ላይ የተመሰረተ ፍቅር ዕድሜው አጭር ነው፡፡ ከአበራ ጋር ንግዱን የጀመሩ ሰሞን ፍቅራቸው ሌላ ነበር። እየዋለ እያደር ሱቃቸው ሲደረጅ፣ ጠቀም ያለ ገንዘብ መምጣት ሲጀምር፣ እንደሻው ተስገበገበና፤ ሞቅ ባለው የሽርክና ፍቅራቸው ላይ ቀዝቃዛ
ውሃ ቸለሰበት፡፡
የዚያን ዕለት አበራን የተናገረው ንግግር ትዝ አለው፡፡ “አበራ እስከዛሬ ድረስ የወሰድከው ሳይታሰብ፤ ያዋጣኸውን ገንዘብ በጥሬው እመልስልሃለሁ፡፡ ግድ የለም እኔ ልጐዳ” በማለት ነበር በድንጋጤ ያስበረገገው፡፡
“እና ሱቁን የግልህ ብቻ ልታደርገው?” አበራ በንዴት እየተንቀጠቀጠ፡፡
“የንግድ ፈቃዱ የግሌ መሰለኝ፡፡እዚህ የምፍጨረጨረውም በግሌ
አንተም ከዚህ በላይ ልትጐዳኝ የምትፈልግ መሆኑን እያየኽው
አይመስለኝም” ቁርጡን ነገረው፡፡
“እሺ እንደሻው እግዚአብሔር ለሁላችንም የሥራችንን ይስጠን፡፡ አንተ ግን ሰው አይደለህም! እባብ ነህ! ያንተ ነገር በቃኝ!ሥጋዬም አይደለህ፡፡ በቃኝ! በቃኝ!” እያለ እየተማረረ እየተንቀጠቀጠ
ከሱቁ ወጥቶ የሄደው ትዝ አለው፡፡ በዚሁ ሀሳብ መሀል ግን...
የትህትና ወንድም መሆኔን እወቅ!” ለሠራኸው ሥራ በዚህ ብቻ የምንላቀቅ እንዳይመስልህ! እስከመጨረሻው እፋረድሃለሁ!!” በማለት ፎከረበት፡፡

በዚህ ጊዜ እንደሻው አመዱ ቡን አለ፡፡ እሱ እንደሆነ ትህትናን ከነመፈጠሯ ነበር የረሳት፡፡ አሁን ግን ጉድ ሊፈላ ነው፡፡ የሚበቀል ወንድም አላት ለካ !!
👍3
ይህ ወጣት እንደማይምረው አወቀ፡፡ የሰራው ሥራ ትዝ አለው። ትህትና መጣችበት፡፡ ልጁን አየው፡፡
“እንዴት ነው የሚመሳሰሉት?” በሃሣቡ፡፡
“አበቃልኝ እንደሻው!! ምን ይሻለኛል?” በዚህ በጭንቀት ውስጥ አንድ ሃሣብ ብልጭ አለለት፡፡ ጋርጠው! ፊቱ መጥቶ ተጋረጠ፡፡ ከአሁን በኋላ ፋታ ሲሰጠው፤ አድፍጦ የሚገድለው መሰለው፡፡ ስለዚህ?
“ሳይቀድመኝ ልቅደመው” ሲል ወሰነ፡፡ ገላጋዩ ሲተራመስ ቀስ ብሎ የሚላላክለትን ጩሎ ጠራው፡፡ ጩሎው መጣ፡፡
“ጋርጠውን በአስቸኳይ ይፈልግሃል በለው” ልጁ እንደተላከው መልዕክቱን ሊያደርስ እየበረረ ሄደ፡፡ የሰው ግርግር ሳይቀንስ፤ አንዱዓለም ከአካባቢው ሳይርቅ፤ ጋርጠው ከች አለ፡፡
“እንዳይሞት እንዳይድን አድርገህ!!” ሃምሳ ብር አስጨበጠው፡፡
“እንዳልከው!!” ሃምሣ ብሩን ላጥ አድርጐ ኪሱ እየከተተ፡፡
ከዚያም ገላጋይ መስሎ ተቀላቀለና አንዱዓለምን በሥውር መከታተሉን
ቀጠለ፡፡

ግርግሩ ከበረደ በኋላ አንዱዓለም በእልህና በቁጭት እንደተዋጠ
ወደ አምባሳደር ሲኒማ ቤት ጉዞ ጀመረ፡፡ ከኋላው ጋርጠውን የመሰለ ጅብ እንዳስከተለ አላወቀም፡፡
የጋርጠው ሰውነት የሚያስፈራ ነው፡፡ በሬ
የዋጠ ነው የሚመሰለው፡፡ የሰው ዝሆን....
አንዱዓለም እስከ ምሽቱ 3፡ዐዐ ሰዓት ድረስ እዚያ ኢትዮጵያ ሆቴል አካባቢ ከጓደኞቹ ጋር ሲጫወት ካመሸ በኋላ ወደ ቤቱ ሊሄድ ተሰናበታቸው፡፡ ጋርጠው በንቃት ይከታተለዋል፡፡ “ኦርማ ጋራዥ አካባቢ ሲደርስ፤ በዚያ በጨለማ ውስጥ፤ መልኩ እራሱ እንደጨለማው የጨለመ
ግዙፍ ሰው ከየት መጣ ሳይባል፤ በከፍተኛ ምት ማጅራቱን አደቀቀው፡፡

አንዱዓለም ህሊናውን ከመሳቱ በፊት
“እንደሻውን መድፈር ማለት ሞት ማለት መሆኑን እወቅ!”
የሚል አስፈሪ ድምጽ መስማቱና ከዚያም መኪና ገጭቶት መሄዱን ነው የሚያስታውሰው፡፡
ጭውው.... አለበት፡፡ የሆነ ጥቁር ነገር ጋረደው፡፡ ከዚያ በኋላ የሆነውን አያውቅም፡፡ ጋርጠው የተሰጠውን ግዴታ በሚገባ ከተወጣ በኋላ በፍጥነት ከአካባቢው ተሰወረ፡፡ በዚያን ሰዓት ከመንገድ ዳር ቱቦ ውስጥ ሆኖ በቃተተ ድምጽ
“ድረሱልኝ!” የሚል የጣዕር ጩኸት የሚያሰማ ሰው ድምጽ የሰሙ ሁለት
መንገደኞች ጠጋ ብለው ቢመለከቱ፤ እዚያ የቆሻሻ መውረጃ ቦይ ውስጥ
በአፍ በአፍንጫው ደም የሚፈሰው ወጣት ተመለከቱ፡፡
በሁኔታው ደንግጠው የእርዳታ ድምጽ ሲያስተጋቡ፤ ሰዎች ከግራና ከቀኝ ብቅ ብቅ እያሉ ወደዚያ ይሮጡ ጀመር፡፡ ትርምሱ ሌላ ሆነ፡፡ ለእርዳታ ከመጣው ሰው መካከል እንዲት ሴት የተመታውን ልጅ ማንነት አጣራችና እሪታዋን አቀለጠችው....
“ወይኔ አንዱዬ.... ወይኔ ....” ያዙኝ ልቀቁኝ አለች። የሂሩት ጓደኛ ሜርኩሪ ነበረች፡፡ ከዚያም እሩጫ በሩጫ ሆነ፡፡ ወዲያውም የፖሊስ አንቡላንስ መኪና ደረሰና የተመታውን ጉዳተኛ ይዞ ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በረረ፡፡
በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሪከቨሪ ክፍል ገብቶ፤ አስቸኳይ የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ ተደረገለት፡፡ ስለደረሰው አደጋ እንዲነግሯት ሜርኩሪ ለሂሩት ሰው ልካባት ስለነበረ በጠዋቱ ከች ብላለች ። የአንዱአለም የወንድና የሴት ጓደኞቹ በጠዋቱ ተሰባስበው ውጤቱን በመጠባበቅ ላይ ናቸው፡፡ በሁኔታው የተደናገጡ ይመስላሉ። እንደዚያ ተሰባስበው ውጤቱን በመጠባበቅ ላይ እያሉ፤ ብዙ ደም ስለፈሰሰው ደም
የሚያስፈልገው መሆኑ ተገለጸላቸው፡፡ በዚህ ጊዜ እርስ በርሳቸው ይተያዩ
ጀመር፡፡
“እኔ አለሁ” የሚል ጠፋ፡፡ ወሬ ለማዳመቅ እንጂ ትንሽ መስዋዕትነት ከፍሎ ፤ ትልቁን የስው ልጅ ህይወት ለማዳን “ አለሁ”
የሚል ታጣ፡፡ ሂሩት እንደዚያ እየጮኽች ስትመጣ፤ ደም ሳይሆን ነፍሷን
የምትሰጥ ነበር የምትመስለው፡፡ድምጧ ጠፋ፡፡
“ለምን እህቱን አንጠራትም?” አለ ትህትናን የሚያውቃት ጓደኛው የሁሉንም ጭንቀት ተመልክቶ ::
“በጣም ጥሩ ነው እንዲያውም የእህቱ ደም ይሻለዋል” ደም ለመስጠት ያልፈለገ ሌላ ጓደኛው፡፡የራሱን ደም መስጠት ባንችል እንኳን እህቱን በጠዋቱ ጠርተን
ከምናስደነግጣት ለምን
አንገዛም?” አለች ሜርኩሪ ያመጣችውን አዲስ ሃሳብ እንደሚቀበሉ በመተማመን፡፡

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
አትሮኖስ pinned «#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ ፡ ፡ #ክፍል_ሰላሳ_ሁለት ፡ ፡ #ድርሰት_በትክክል_ገና እቅዳቸው በአሳዛኝ ሁኔታ መክሸፉን፤ መክሸፍ ብቻም ሳይሆን የሷና የሻምበል ብሩክ ፍቅር እስከ ወዲያኛው ዳግም ላይጠገን እንክትክት ብሎ መሰባበሩን ስትሰማ አዜብ ክፉኛ ደነገጠች፡፡ ምን የማይሆን ምክር መክሬ ጉድ ያደረኳት፤ በሚል ጸጸት ተቃጠለች፡፡ ለዚህ ችግር መንስኤው እሷ እንደሆነች ሁሉ “እኔ ነኝ ጉድ ያደረኩሽ ትሁትዬ፡፡…»
#ሰመመን


#ክፍል_አርባ_ስምንት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

...ዮናታን ቤታችው ሲደርሱ፥ ሞኒካ የስብሰባውን ሁኔታ ለመስማት ጓጉታ በሕንፃው መናፈሻ በኩል ቁልቁል እየተመለከተች መምጫቸውን በመጠባበቅ ላይ ነበረች ።

“ እንዴት ነው ? ” አለቻቸው ፡ ከፊቷ ላይ የማይጠፋ ፈገግታዋን ብልጭ አድርጋ "

“ ደስ የሚያሰኝ ስብሰባ ነበር " በብዙ ሰዎች ላይ ቀና ስሜት አሳድረናል” አሏት፡እጅዋን ይዘው ወደ ውስጥ እየገቡ ጥናቱንም ቢልልኝ በጥሩ መልክ አቅርበውታል የጥናቱን ጽሑፍ ከእሳቸው ተውሼ ሰሞኑን አመጣልሻለሁ”

ሞኒካ ስብሰባው ላይ ለመገኘትና በአቤል ላይ የተካሔደውን ጥናት ለማዳመጥ ከፍተኛ ጉጉት ነበራት ጥናቱ የቀረበው በአማርኛ ስለ ነበር በደንብ የማትሰማው ቋንቋ ሆኖባት ነው የቀረችው።

“ አካዳሚክ ኮሚሽኑስ ምን አለ ? ” ስትል ጠየቀቻቸው "

“ የእነሱ መደበኛ ስብሰባ ገና ከአራት ቀን በኋላ ነው ።ሆኖም ስብሰባችን ላይ የነበሩት የኮሚሽኑ አባላት በግል ተስፋ ሰጥተውኛል ። እና ጥሩ ውጤት እጠብቃለሁ ።

ዮናታን ከሚስታቸው ጋር እያወሩ ልባቸው አቤልን ለማየት ጓጉቶ ነበር • ሳሎን ውስጥ ሲያጡት የት እንዳላ
ለማወቅ ሞኒካን መጠየቅ አላስፈለጋቸው? በቀጥታ ወደ መጻሕፍት ክፍላቸው ሔዱ ። በሩን በዝግታ ከፍተው
ሲገቡ'አቤል በሚያነበው መጽሐፍ ክፉኛ ተመስጦ አገኙት ።
ሊረብሹት አልፈለጉም ። በሩን በዝግታ ዘግተው ለመመለስ ቢያስቡም እጃቸው የበሩን እጀታ መጎተት አልቻለም ለአቤል አንዳች ነገር ሊነግሩት ፈለጉ ። ቀን ምን እንደሚነግሩት ወይም ደስታቸውን እንዴት እንደሚገልጹለት አያውቁም ነበር። አቤል በእሱ ጉዳይ ስብሰባ መካሔዱን አያ
ውቅም ። ጉዳዩ ክብደት ተሰጥቶት አደባባይ መቅረቡ በአንድ በኩል ሊያስደስተው ቢችልም በሌላ በኩል ደግሞ የሚደብቀው የዐይን ፍቅር መጋለጡ ስሜቱን ሊጎዳው ስለሚችል፥ ይህን በማመዛዘን ዮናታን ሆነ ብለው ነበር ያልነገሩት አሁንም ይህን ሊነግሩት አልፈለጉም። እንዲሁ ብቻ በፈገግታ የደስታ ስሜታቸውን ሊያስተላልፉለት አሰቡ ።

ወደ ውስጥ የጫማቸው ድምፅ አቤልን ከተመሰጠበት አባነነውና ካቀረቀረበት መጽሐፍ ቀና አለ ። ፈገግታቸውን
ሲያይ ፡ ምን አገኙ ይሆን ? ብሎ አልተደነቀም ። ንባብ ላይ ተቀምጦ በማግኘታቸው የተደሰቱበት መሰለው ።
“ እንደምን ውለሃል ? ” አሉት ፡ እንዲህ የሳበው መጽሐፍ ምን እንደሆነ ለማወቅ ዐይናቸውን ወደ ርዕሱ እየወረወሩ
ደኅና ፡ ሲገቡ አልሰማሁዎትምኮ ” አላቸው ፡ የደረሰበት ገጽ እንዳይጠፋው ማዕዘኑ ላይ እያጠፈ ።

የሚያነበው “ ማን አገንስት ሄምሰልፍ ! ” “ ሰው ራሱን ሲጻረር ! የሚለው የዶክተር ሜኔንገር መጽሐፍ ነበር " ዮናታን ይህን አርዕስት ሲያዩ ደነገጡ ። ካልጠፋ
መጽሐፍ ይኽን ለምን መረጠው ? የሚል ጥርጣሬ አደረባቸው፤ፈገግታቸው በአንድ አፍታ ጠፋ ። ፈጥነው ሊጠይቁት ግን አልደፈሩም ። ከውጭ ይዘውት የመጡት የደስታ ስሜት ከውስጥ ጥቀርሻ ሲለብስ ተሰማቸው ።

“ ወደ ውጭ ወጣ ብለን እንናፈስ ? ዛሬ ንባብ ላይ ብዙ የቆየህ ይመስለኛል ” አሉት ' ስሜቱ በመጥፎ ነገር ተወጥሮ ከሆነም ወጣ ብሎ መናፈሱ ይሻለዋል በሚል ግምት ።

“ በደስታ!” አላቸው ከተቀመጠበት እየተንጠራራ ።

አመላለሱም ሆነ የፊቱ ብርሃን ከውስጡ መጥፎ ስሜት የወጠረው ሰው አይመስልም ። ዮናታን በግምታቸው ግራ
ተጋቡ ።

ሊብሊንግ ፡ ሽርጥሽን አውልቂና ወጣ እንበል ”አሏት ሚስታቸውን ወደ ሳሎኑ ተመልሰው ።

ሞኒካ ቤት ውስጥ ከሆነች ከወገቧ ነጭ ሽርጥ አይጠፋም።

“ አቤልስ ይመጣል ? ”አለቻቸው ፈቃደኛነቱን ለማረጋግጥ ።

“ አዎ ፡ እወጣለሁ ብሏል ” አሏትና " ወደ ጆሮዋ ጠጋ ብለው ፥ የዛሬ ውሎው እንዴት ነው ? ” አሏት ፡

የመጽሐፉ አርዕስት እየከነከናቸው ነበር
“ ደኅና ነው የዋለው ። እንዲያውም ንባብ ከመጀመሩ በፊት እሱ ባደገበት አካባቢ ያለውን የጋብቻ ሥነ-ሥርዓት ሲያጫውተኝ ነበር ” አለቻቸው ሽርጧን እየፈታች ።

ዮናታን ውጭ ወለው ቤት ሲገቡ ስለ አቤል ሁኔታ መጠየቅ ልማዳቸው ነበር ። አቤልም ዮናታን ቤት መኖር ከጀመረበት ጊዜ አንሥቶ ያሳየው ለውጥ ቀላል አልነበረም » እብሯቸው ሲኖር ሳምንት ሆኖታል ። ከእራሱ ጋር መታረቅ ጀምሯል ለውጡ የሞኒካ የድካም ውጤት ነው
ማለት ይቻላል ።

ለመጀመሪያው ሁለት ቀን አቤል ራሱን ገዝቶ ቤት ውስጥ መቀመጡ በጣም አስቸግሮት ነበር " ትዕግሥት በሐሳቡ
እየመጣችበት ብረር ብረር ይለው ነበር ። ሲጠላው የነበረው ዩኒቨርስቲ ይናፍቀዋል ትንሽም ቀለል የሚለው እስክንድር መጥቶ አጫውቶት ሲሔድ ነበር ።

ዮናታንና ሚስታቸውም ይህን ችግሩን ሳይረዱለት አልቀሩም ። ሐሳቡን ከትዕግሥትም ሆነ ከሌላ መጥፎ
ስሜት ለማዘናጋት የተጠቀሙበት ዘዴ መንፈሱ ለሥራ መወጠር ነበር ለቀን ተቀን እንቅስቃሴው ፕሮግራም
አውጥተውለታል ። ሞኒካ ምግብ በምታበስልበት ሰዓት አብሯት ሆኖ የምግብ አሠራሯን እያጠና በአንዳንድ
ማኅበራዊ አርዕስቶች ላይ ይወያያሉ በቀን የተወሰነ ሰዓት እሷ ጀርመንኛ ታስተምረዋሶች ። እሱም በፈንታው
ለተወሰነ ሰዓት አማርኛ ያስተምራታል ። ይህ አቤል ከመምጣቱ በፊት የዮናታን ሥራ ነበር ። ስለዚህ ማታ ማታ ሞኒካ ቀን የተማረቻቸውን አንዳንድ አዳዲስ የአማርኛ ቃላት ስትናገር፥ ዮናታን ወደ አቤል እየመተለከቱ ፥ ጥሩ ረዳት አገኘሁ እንዲያው ከኔ የተሻለ ዘዴ ሳይኖርህ አይቀርም ” በማለት ይክቡታል ። በመጀመሪያ ለንባብ የተመደበለት የተወሰነ ሰዓት ነበረው ውሎ ሲያድር ወደ ንባቡ ፍቅር ሲመለስ ግን፡ለንባብ ከተቀመጠበት ስፍራ የሚነሣው .
በቀስቃሽ ሆነ ። ከንባብ ውጭ ለመዝናናት ያህል በቤት ውስጥ የሚያገኛቸውን የጀርመን ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ሥዕላዊ መግለጌ የያዙ መጻሕፍት ማገላበጠት በመንፈስ
ውስጥ የጥሩ ሕይወት ስሜት ያሳድርበት ነበር ። የሀገር ውስጥና የውጭ ሙዚቃ በሙሉ ጆሮው ሰምቶ ለማድነቅ
የቻለው በዚህ ሳምንት ውስጥ ነው ። ትርጉሙም ሆነ ጣዕሙ ሲገባው ያልቻለውና ዮናታን የሚያደንቁትና በተመስጦ ያሚያዳምጡት፡የእነ ቫግነርና ቤትሆቭን ክላሲካል ሙዚቃ ነው "
ቤት ውስጥ ሙዚቃ ማዳመጡ ቢያስደሰተውም አንዳንዴ ትካዜ ስለሚጫነው ፥ ለመቆጠብ ወይም ብቸኝነት በማያጠቃው ሰዓት ብቻ ለማዳመጥ ተግዶ ነበር ።

ቀን በዚህ ዐይነት ውሎ ወደ ማታ ላይ ሦስቱም ነፋስ ለመቀበል ወደ ከተማው ጸጥታማ ቦታዎች ብቅ ይላሉ ።
አሰልሠው ሲኒማ ይገባሉ ። ይህን የመሰለው የሕይወት እንቅስቃሴ አቤልን ከብቸኝነት ስሜቱ በማዘናጋት ሐሳቡ
አንድ ነገር ላይ ብቻ በማተኮር እንዳይሠቃይ ከፋፍሎታል ። ያም ሆኖ ትዕግሥትን እያሰበ ሳይጨነቅ አያድርም
ግን ጭንቀቱ እንደ ቀድሞው አልነበረም ፡ በሥራ በተወጠረ አእምሮ ወይም ደክሞ እንቅልፍ በፈለገ ጭንቅላት ስለሆነ የሚያስባት ፥ ያን ያህል አይረበሽም ።

አቤል ከብርቅነሽ ቀጥሎ በሕይወቱ የገጠመችው ግልጽ ሴት ሞኒካ ነች ። በአንድ ምሽት ዕድሜም ቢሆን
የብርቅነሽ ትሑትና ግልጽ ተፈጥሮ በልቡ ተቀርጿል ። ምናልባትም የብርቅነሽ ግልጽነት ከማይምነቷ ጋር የተያያዘ
የልብ ክፍትነትና የጥሬነት ውጤት ሊሆን ይችላል ። የሞኒካ ግልጽነት ግን ምሁራዊ ጥልቅ ትርጉምና ድምቀት አለው ። ከአኳኋኗ መረዳት እንደሚቻለው “የምንፈጽመው ጥሩም ሆነ መጥፎ ነገር የህልውናችን ነጸብራቅ ነው ፤ ስለሆነም
እኛነታችንን ደብቀን መሠቃየት የለብንም ፤ መጥፎ የምንለውን አምቀን ጥሩ የምንለውን ብቻ የምንተነፍስ ከሆነ
ውስጣችን ገምቶ ደማችን ይደፈርሳል የምትል ትመስላለች አቤል በቀላሉ ነው የተግባባት
👍4
አንዳንዴ በንጹሕ ጨዋታዋ ሲመሰጥ ! ስሜቱን ደብቆ የሚወጣጠር ተፈጥሮውን
ይረግማል። እያደር ራሱን መደበቅ ከማይችልበት ደረጃ እየደረሰ ነበር " የእሷ ግልጽነትና ማብቂያ የሌለው ጣፋጭ
መስተንግዶ ሳይወድ በግድ ልቡን እየከፈትበት መጥቷል "

በተለይ አንድ ቀን ሞኒካ ከዮናታን ጋር ስላላት ግንኙነት ግልጽ ሆና ያጫወተችው ነገር ጭንቅላቱ ውስጥ ተቀርጾ ቀርቷል ። ዮናታን ለንባብም ሆነ ለጥናት ሥራ ቤታቸው ውስጥ አንዴ ከተቀመጡ ወጣ ብሎ የመዝናናቱ ነገር አይታያቸውም ። የሕይወታቸውን አብዛኛውን ክፍል ለኣካዳሚክ ጥረት ስለሰጡ ደስታ የሚሰጣቸው ከጠረጴዛ ትጣብቆ መዋሉ ነበር ። ሞኒካ ደግሞ መጫወት ትፈልጋለች መዝናናት ትፈልጋለች ! ለውጥ ያምራታል ይህ ልዩነት ለተወሰነ ዓመታት አብሮአቸው ቆይቷል ። ከዚህ በላይ የከ
በደው ልዩነት ደግሞ በግብረሥጋ ግንኙነት ረገድ ያለው ነበር " የዮናታን የጠነከረ የአካዳሚክ ሕይወትና የዕድሜ
ያቸው መግፋት የወሲብ ፍላጎታቸውን ስለሚያዳክምባቸው ጥማታቸው ከሞኒካ ጋር እኩል አይሆንም " ቀዝቃዛ ይሆኑባታል ። አንዴ ሞኒካ መኝታዋ ውስጥ ገብታ ዮናታንን በመጠበቅ ብዙ ቆየች • በመጨረሻም በሽታ ዕርቃኗን ከመኝታዋ ወጥታ ወደ መጻሕፍት ክፍሉ ሔደች ። ዮናታን መጽሐፍ ላይ እንዳቀረቀሩ ነበሩ ስሜቷ ተወጣጥሮ ቢያሠቃያትም ኅሊናዋን ስላልሳተች፡እንዳትረብሻቸው ፈርታ ወደኋላ
ተመለሰች “ ነገር ግን ብሽቀቱ ልቧ ውስጥ እንደ ተቀበረ ስለ ነበር ሳሎኑ ጠረጴዛ ላይ ያገኘችውን የዕብነ በረድ የሲጋራ መተርኮሻ በደመ ነፍስ አንሥታ ስትወረውር የብፌውን መስታወት ከሰከሰችው ደገመችና ብፈው ወስጥ
የነበሩትን ስኒዎች አንከታከትቻቸው "

ዮናታን ደንግጠው ከጥናት ክፍቸው እየሮጡ ሲደርሱ ሚስታቸው ዕርቃኗን ተገትራ ፡ የመስታወቱ ድቃቂ መሪት
ተዘርግፎ ተመለከቱ ጸጉሯ ተበታትኖ ፡ ነጭ ፊቷ ፍም መስሎ ሲያዩዋት ልዩ ፍጥረት መሰለቻቸው " ምን ሆንሽብኝ ሊበሊንግ ? ” አሏት ። ዐይኗን ከማፍጠጥ ሌላ ፈጥና አልመለሰችላቸውም ። የማይጠገብ ትሕትናዋን ያህል ' የተናደደች እንደሆን አያድርስ ነው • የቤት ዕቃ አይተርፋትም “ በብሽቀት ጊዜ ሰው እንዳታስቀይም ወይም እንዳትጎዳ የስሜት እሳትን የምታበርዳው ዕቃ በመሰባበር ነው ። ያን ዕለት ችግሯን ለዮናታን ፍርጥርጥ አድርጋ ነገረቻቸው ። ከዚያ ጊዜ በኋላ፥ ዮናታን የምሽት የንባብ ጊዜያችውን ቀይረው እሷን ቀድመው መኝታ ውስጥ እየገቡ ይጠ
ብቋት ጀመር ።

አቤል ይህን ከእሷው አፍ መስማቱ፡ ነው ያስደነቀው ።ድርጊቷን ስትነግረው በልጅነቱ ሴት አያቱ ሴት ልጅ ካልተገረዘች ዕቃ ትሰብራለች ” የሚሉት ፈሊጣቸው ነበር ትዝ ያለው ሞኒካ ለአቤል ሌሎችም ነግሮች በግል ባጫወተችው ቁጥር በዚህ ጥቂት ቀናት ውስጥ ስሜቱ በቀላሉ ታዛዥ እየሆነ መጣ ። አቤል በሞኒካ የሚደነቅበት ሌላዉ ነገር ደግሞ የቤት ውስጥ እንቅስቃሴዊ ነው ። ዐርፋ አትቀመጥም ። ደስታዋ የሚመነጨው ከሥራና ሰውን ከማስደሰት ይመስላል።

ሞኒካ ከሀገሯ እንደ መጣች ለሁለት ዓመት ያህል በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በነርስነት ሠርታለች። ነግር ግን ከጊዜ
በኋላ የመድኃኒት ሽታ ለጤንነቷ ስላልተስማማት ፥ ይኸን ስራዋን ለማቆም ተገደደች። ያ ሲቀር የቤት አስተዳደር ሥራ
ኮስተር ብላ ያዘች ።ለእሷ ትልቁ ሥራዋ ምግብ ማብሰል አይደለም ። ለቤቷ ሕይወት ለመስጠት ነው የምትደክመው
ለዐይን እንዳይሰለች ትጥራለች ። ጥልፍ የመሳሰሉት የእጅ ሥራዎቿ አንድ ግድግዳ ላይ ከተወሰነ ጊዜ በላይ ኣይቆዩም ።
ይለዋወጣሉ ። የቤት ውስጥ የአበባ ተክሎቿን መከርከምና ውሃ ማጠጣት ሕፃን ልጅ አቅፎ እንደሚጫወት ነው የሚያስደስታት ። ከአልጋ ጀምሮ የቤት ዕቃዎች አቀማመጥ በተለያየ ጊዜ ትለዋውጣለች ። የመኖሪያ ቤት ዕቃዎች አቀማመጥ መቀያየር በነዋሪው ላይ ምን ያህል መንፈስ የማደስ ኃይል
እንዳለው ታውቃለች ። ዐይን በቀላሉ ይወዳል ፤ ዐይን በቀላሉ ይጠላል ፤ ዐይን በቀላሉ ይታለላል ። ዐይን ከረካ፡ የውስጥ
ስሜት በጥላቻ አይደፈርስም ። መኖሪያ ቤቱ የሚስብ ከሆነ ልብ ወደ ውጭ አይኮበልልም ። ይህን መመሪያዋ አድርጋ
የያዘች ትመስላለች ሞኒካ ። ቤቱን አዘገጃጅታ ስትጨርስ መጽሐፍ ታነባለች የየወቅቱን የውጭ መጽሔቶች እያነበበች ለዮናታን ሥራ የሚጠቅም አርዕስት ስታገኝ መርጣ ታስቀምጥላቸዋለች ። ጀርመን ካሉት ዘመዶችዋ ጋር ደብዳቤ
መጻጻፍ የሚያስደስታት ጊዜ ማሳለፊያዋ ነው ። አከታትላ ስትጽፍ አቤል እየገረመው ምን እንደምትጽፍ ለማወቅ
ይጓጓል ።

ይህ ሁሉ የሞኒካ ሁኔታ በአቤል ላይ በአጭር ጊዜ ውስጥ ያሳረፈበት የአስተሳሰብ ተጽዕኖ ቀላል እንዳልሆነ
ዮናታን በሚገባ ይከታተላሉ ። ሕይወትን ከመናቅና ከመጥላት ሕይወትን ወደ ማድነቅ እየተሸጋገረ መሆኑን ከኣንዳንድ ድርጊቶቹና ጨዋታዎቹ ለማወቅ ችለዋል (ዛሬም ትንሽ ያስደነገጣቸው ይዞ ያገኙት ከወትሮው ለየት ያለ ዐይነት መጽሐፍ ነው

“ መሔድ እንችላለን” አላቸው አቤል ከመኝታ ክፍሉ ወደ ሳሎን ብቅ ብሎ ጸጉሩን ሲያበጣጥር ነበር የቆየው ።
ዮናታንና ሚስታቸው ተሰናድተው እሱን በመጠበቅ ላይ ስለ ነበሩ፥ ወዲያው ተያይዘው ወጡ ። አቤል ፊት ላይ ከወትሮው ለየት ያለ ይነበብ ነበር ። ምን ተሰምቶት ይሆን ?ዮናታንና ሞኒካ ስሜቱን መጋራት ፈለጉ። ሆኖም ደረጃውን ለመውረድ አሳንሰሩ ውስጥ እስኪገቡ ድረስ ምንም ቃል አልተነፈሱም ።

የዛሬው ንባብህ እንዴት ነበር ? ሲሉ ዮናታን ፈገግ ብለው ጠየቁት ።ጥሩ ነበር እንዲያውም ... ” ብሎ አቋረጠ ።
የሚቀጥለውን ለመስማት ቢጠብቁትም መልሶ ዋጠው፡፡ መደበቅ ፈልጎ ሳይሆን እንዴት እንደሚነግራቸው ተቸግሮ
ነበር ።

ያንን ይዘኸው የነበርከውን መጽሐፍ እንዴት ወደድከው ? ” ሲሉ ዮናታን ደግመው ጠየቁት ።

“ እንዳጋጣሚ መጽሐፍ ስመርጥ ነው ያገኘሁት ። ገና “ማን አጌንስት ሄምሰልፍ” ( የ ሰው ራሱን ሲጻረር ) የሚ
ለውን አርዕስት ሐሳቤ ውስጥ ማን ፎር ሄሳምሰልፍ (ሰው ራሱን ሲያፈቅር ) በሚል አርዕስት የመጻፍ ስሜት
አደረብኝ ። እንዴት እንደሆን እንጃ ! ላሳስበው ስሜቴን ቀሰቀሰብኝ ። ስለዚህ " ሰው ለራሱ ወዳጅ የሚሆንበትን ሁኔታ
ለመጻፍ በመጀመሪያ ሰው ለራሱ ጠላት የሆነባቸውን ሁኔታዎችና ምክንያቶች ማወቅ ይጠቅማል ብዬ ነው-እሱን
በማንበብ ላይ ያለሁት ። እና እንዲያውም ከማንበብ ወደ መጻፍ ልሸጋገር ሳይሆን አይቀርም ።

ዮናታን ደስ አላቸው ። ከአቤል ጋር የሚያወሩት በአማርኛ ስለ ነበረ ለሞኒካ ተረጐሙላት ።

“ በእርግጥ ? ” አለች በእንግሊዝኛ ፡ የእሷም ደስታ ገደብ አጥቶ ዐይኖችዋን እያቁለጨለጨች ።

በእርግጥ ! በማለት አቤል ጨዋታው ውስጥ እሷም እንድትሳተፍ በእንግሊዝኛ ቀጠለ። “ በዚህ አርዕስት የመጻፍ ሐሳብ ጭንቅላቴን ወጥሮ ይዞታል ። አሁን ገና ሳልጀምረው ችግር የሆነብኝ የጊዜ ጉዳይ ነው መሠረት የሚሆኑኝን መጽሐፎች አንብቤ ለመጻፍ ብዙ ጊዜ ያስፈልጋል ።
እና ጊዜ የሚያንሰኝ መሰለኝ ። ”

ከአሳንሰሩ ወጥተው ወደ መኪናቸው አመሩ ።

“ ገድየለህም እስቲ ጀምረው ” አሉ ዮናታን ፥ የጊዜው ነገር አይቸግርም ። መቼም ይኸን ሴሚስተር ትምህርት
ህን ማቋረጥህ የታወቀ ነው ። ስለዚህ እስከ አዲሱ ዓመት ድረስ ስድስት ወር ያህል ነጻ ጊዜ ይኖርሃል ።
በሰበቡ ትምህርቱን የማቋረጡን ውሳኔም መናገራቸው ነበር ። አቤል ግን ይህንን ቀድሞም አላጣውም ። የሁለተኛው ሴሚስተር ትምህርት እንደ ተጀመረ ያውቃል ። የናታን ቤታቸው ያመጡት አንዴ ቢሮአቸው ጠርተውት ፡ “ ትምህርትህን ማቋረጥ አለብህ ” ያሉትን ነገር ተግባራዊ ለማድረግ
👍3
መሆኑ እየገባው መጥቷል ። ሆኖም ጥረታቸው ሁሌ ለእሱ ጥቅም መሆኑን በማወቁ ውሳኔአቸውን ለመቀበል በቅቷል ። ለወላጆቹ ደብዳቤ ሲጽፍ እጁን ይዞ ያስቸገረው
“ ትምህርቴን ለጊዜው አቋርጨአለሁ የሚለው ዐረፍተ ነገር ነበር ። ሲውል ሲያድር ግን ነገሩን አቅልሎ እንዲመለከ
ተው ተገዷል ።
ዐውቃለሁ ። ግን ስድስት ወሩም የሚበቃ አይመስለኝም ። አእምሮዬ የጀመረውን ሐሳብ ሳስበው ብዙ ነው ? አላቸው ።

አይዞህ ኣንተ ጽሑፉን ከጀመርክ ጊዜን ወደኋላ የሚጎትት ነገር እንፈጥራለን ” አሉት ዮናታን ፣ ደስታው ለቀልድ ጋብዞአቸው ።

አቤል ፈገግ አለ ። ጤናማና ልባዊ ፈገግታ! የሞኒካም ፊት እንደዚያው ነበር
ዛሬ ለለውጥ ያህል ኳስ ጨዋታ ብንመለከትስ ? ”አሉ ዮናታን መኪና ውስጥ ከገቡ በኋላ የሚስታቸውንና
የአቤልን ፈቃደኝነት በሚጠይቅ ድምፅ ።

ሁለቱም በፈገግታ ፈቃደኝነታቸውን ግለጹላቸው ። ዮናታንና ሞኒካ ዐልፎ ዐልፎ ኳስ ጨዋታ መመልከት ይወዳሉ ።

“ ወድያውም ፎቶግራፋችን ደርሶ እንዶሆን እግረ መንግዳችንን እንጠይቅ ” አለች ሞኒካ ።

ሦስቱ አንድ ላይ ፎቶ ተነሥተው ፊልሙን ለማሳጠብ ሰጥተው ነበር ። አቤልም ይህንኑ ፎቶ ለመሳክ በማሰብ ለወላጆቹ የጻፈውን ደብዳቤ ገና አልሰደደውም ።

ፎቶው ቤት ሲጠይቁ ደርሶላቸው አገኙት ፡ ግሩም ሆኖ ነው የታጠበው። አቤልን ከመሐላቸው አቁመው ባልና ሚስቶቹ፤ ትከሻውን አቅፈው ነበር የተነሱት ። በስተጀርባቸው የአትክልት ስፍራ ስለ ነበረ ለፎቶው ልዩ ድምቀት ሰጥቶታል ። አቤል ፎቶውን ሲመለከት በሐሳቡ የመጠበት
እናቱ ነበሩ ። “ ትደሰት ይሆን ? ወይስ ልጄን ቀሙኝ ብላ ትቀና ይሆን ? ” ሲል አሰበ ።

ነገ ጠዋት ከደብዳቤው ጋር ወደ ወላጆቼ እልከዋለሁ፡ አላቸው ፍርጥም ብሎ ።

ጥሩ አሉና ዮናታን ፥ ቦርሳቸውን አውጥተው ሰማንያ ብር ቆጥረው ፥ ይህንንም ጨምረህ ላክላቸው
አሉት ።

"ምንድን ነው" አላቸው ተደናግጦ።

"ገንዘብ ነፃ ! ” አለችው ሞኒካ ። ሰሞኑን ዮናታንና ሞኒካ ተመካክረው ያሰቡበት ነገር ነበር ።

አቤልን መቀበል ከበደው።

ሥራ ስትይዝ የምትከፍለው ዕዳ ነው ! አይዞህ ” አሉና ዮናታን ቀለዱበተት።

አቤል ምንም አልመለሰም ። ዝምታን መረጠ ። ደስታ ገደቡን ሲያልፍ ቃላ መግለጽ እንደማይቻል ገባው !
እነሱም ‹እሱ ዝምታ እንደ ጋባቸው ሁሉ ጸጥ አሉ ቮልሳቸው ብቻ ማቃሰቷን እላቋረጠችም ።

አቢል ጭንቅላት ውስጥ በይነታ የታጀበ የተላያየ ሐሳብጨ ተፈራረቀበት ። ነገር ግን የአንዱን ጭራ መያዝ አልቻለም ከመኪናዋ ፍጥነት ጋር የሐሳብ ግልቢያ ብቻ !

“ ጋሽ ዮናታን ፤ ነገ ቢሮ ሲገቡ ከዚ በፊት የሰጠዎትን የጥናት ፅሁፍ ወረቀቶች ያምጡልኝ ”አላቸው ሲያስብ ቆይቶ በድንንት ።

“ ለምን ፈለግካቸው? እንደ ገና አርመህ ልትሠራቸው ነው? ”አሉት ዮናታንም አጠያየቁ ጤናማ መልክ እንዳለው በመገመት።

“ ብቻ ያምጡልኝ” አላቸው ሙያ በልብ ነው የሚል ኩራት በያዘ ድምፅ። ”

እሺ በደስታ ! ”አሉትና ዮናታን ትንሽ ቆይተው ሌላስ ከዩኒቨርስቲ የምትፈልገው ነገር የለም ? » ሲሉ ጠየቁት ።

ምን ?” አላቸወ መልሶ ። ነገሩ ቶሎ አልገባውም ። ከኋላ ስለ ተቀመጠ፥ ዮናታን በመስታወት ውስጥ ፊቱን እያዩት ነበር።

ከፈለግክ ትዕግሥትም ትመጣልሃለች” አሉት በአዝጋሚ ድምፅ ። ፊቱን በመጠኑ ሲለወጥ በመስታወት ውስጥ ተመልከቱት ።

“ ምን ታረግልኛለች ? ! እሷ ጠላቴ ነች ። እሷን ማየት ካቋረጥኩ ጀምሮ አእምሮዬ በደንብ መሥራት ጀምሯል አላቸው በሻከረ ድምፅ ።

ዮናታን አመነቱ ። እውነት ሰላም ካገኘ እሷ ብትቀርበትስ ? ብለው አሰቡ ወዲያው ግን ከእስክንድር ጋር የተወያዩት ነገር ሐሳባቸውን አፈረሰባቸው ።

ትዕግሥት ፍቅር እንጂ ጠላትህ አይደለችም ። ጠላትህ ስለ ፍቅር ጠልቀህ እንዳታውቅ ጨቁኖ ያሳደገህ
አካባቢህ ነው ” አሉት ፥ የቢልልኝ ድምፅ ጆሮአቸው ። ውስጥ እየደወለ ።

አቤል መጥፎም ጥሩም አልመለሰም ። አንገቱን እቀርቅሮ እንደገና ፎቶአቸውን ይመለከት ጀመር ።

💥ይቀጥላል💥
👍3
እንኳን ለደብረ ታቦር (ቡሄ) በዓል በሰላም
🥖አደረሳችሁ አደረሰን🥖
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሰላሳ_ሶስት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

..“ይሸጣል እንዴ?” ከመካከላቸው አንዱ፡፡
“አሉልህ እኮ አሁን ወጣ ብለን ብንፈልግ ደማቸውን እንደ ጭማቂ ለመሸጥ የሚንጐራደዱ አይታጡም" ”ሌላው፡፡ ይሄ ደግሞ የገንዘብ መስዋዕትነትን ጠየቀ፡፡ አሁንም ተፋጠጡ፡፡
“አቦ ትጠራ ምን ትሆናለች” ባዩ በዛና ትህትና ይሄንን መርዶ በጠዋቱ እንድትረዳ ፈረዱባት፡፡ ከዚያም ልጁ ሊጠራት እየበረረ ከሆስፒታሉ ወጣ፡፡
እሷ በዚያን ሰዓት አገር ሠላም ነው ብላ ለእናቷ የምትወስደውን ምግብ እያዘጋጀች ነበር፡፡ ወንድሟ ለሷ ለሚወዳት እህቱ ብሎ በዚህች
ስዓት በሕይወትና በሞት መካከል ይገኛል፡፡
በጠዋቱ የተንኳኳውን በር ሄዳ ከፈተች፡፡ ለምን እንደሆነ አላወቀችም ልቧ ሽብር ሽብር አለባት፡፡
“አንዱአለም ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ገብቷል” አላት ጭክን ብሎ።
“ኡ ይ!” ምን ሆኖ!” ጮኸች።
“ሰው ደብድቦት፡፡ አሁን በአስቸኳይ ደም ተጠይቋል” ቁርጡን ነገራት። ከዚያ በኋላ ያደረገችውን አታውቅም፡፡ የሞተ ነው የመሰላት፡፡
የውጭውን በር በርግዳ....
“ኡኡ.... አንዱዬ ...! አንዱዬ....! ወንድሜን!... ወንድሜን!”
ሩጫዋን ቀጠለች። ልጁም ከኋላ ከኋላዋ እየተከተለ ተያይዘው ቁልቁል ይሮጡ ጀመር፡፡ እንደዚያ ራሷን ስታ እየጮኸች ስትሮጥ የሚያያት ሰው በጣም ነበር ያዘነላት፡፡ እንባዋ እንደጉድ ይፈሳል፡፡
ከጥቁር አንበሳ ት/ቤት ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ለመሻገር ከላይም ከታችም መኪና ማየት ሲገባት፤ እንደዚሁ ግብኗን እየበረረች ግማሹን አስፋልት ተሻግራ ደሴቱን አቋረጠችና ወደ ሁለተኛው አስፋልት ጥልቅ ብላ ገባች፡፡
ከዚያ ከላይ ከቴዎድሮስ አደባባይ ቁልቁል እየበረረች የምትመጣው ውይይት ታክሲ በድንገት ጥልቅ ብላ የገባችውን ልጅ ለማዳን ሹፌሩ ፍሬኑን በሃይል ሲረግጠው፤ መኪናዋ ወደጐን ዞረችና ደሴቱ መሐል ገብታ ተቀረቀረች፡፡
እዚያ ታክሲ ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች በድንጋጤ ውሃ ሆነዋል፡፡ ትህትና የዚህ ሁሉ መንስኤ እሷ መሆኗን አታውቅም፡፡
ሩጫዋን አላቆመችም፡፡ ልጁ በተፈጠረው አደጋ ተደናግጦ ጭንቅላቱን
በሁለት እጆቹ ይዞ ቀረ፡፡ ከዚያም ሮጦ ደረሰባትና! እጇን ይዞ ይማፀናት
ጀመር፡፡ አልሰማ አለችው፡፡ ያለው አማራጭ ከኋላ ከኋላዋ መሮጥ ብቻ
ነበር፡፡ ተያይዘው ሆስፒታል እንደ ደረሱ፤ እነዚያ የሆያ ሆዬ ጓደኞቹ ተሰባስበው! ተቀበሏት፡፡
“የት ነው ያለው? ወንድሜ የት ነው? አንዱዬ የታለ? ሞቶ እንደሆን ንገሩኝ” ትለፈልፋለች፡፡ ከስንት ልመና በኋላ እንደምንም ብለው ሊያረጋጓት ሞከሩ፡፡ ከዚያም ሀኪሞች “አይዞሽ ደህና ነው” ብለው ካጽናኗት በኋላ ደም እንድትሰጥ ተደረገ፡፡
“ወንድሜን ዐይኑን ልየው እባካችሁ?” እያለች ፤ እያለቀሰች ብትለምንም “ሪከቨሪ” ስለሆነ መግባት አይቻልም ተባለች፡፡
ቀስ በቀስ ነፍሷን መግዛት ስትጀምር፤
ለአዜብ ስልክ አስደወለችላትና አዜብ መጣች፡፡ አዜብ ሁኔታውን እንዳረጋገጠች...
“ምን መዘዘኛ ነኝ?” የሚል መጥፎ ስሜት ተሰማት፡፡ ሚስጥሩን ስትነግረው በፍፁም የዚህ አይነቱ አደጋ ይደርስበታል ብላ አልገመተችም ነበር። ትንሽ እዚያ አካባቢ ዞር፤ ዞር፤ እያለች ከቆየች በኋላ፤ ሹልክ ብላ ሳትነግራት ወደ ቤቷ ሄደች፡፡
ትህትና ጨንቋት፤ አጽናኝ በምትፈልግበት ሰዓት ላይ ጓደኛዋን ብትፈልግ አጣቻት፡፡ ወዲያና ወዲህ ተዘዋወረች፡፡ ተዟዟረች፡፡ አዜብ ግን የለችም፡፡ በመጨረሻ ላይ እቤት ስልክ ደወለች፡፡ “የለችም” አስባለች፡፡ እየመሸ መጣ፡፡ እንደገና ስልክ ደወለች፡፡ አሁንም የለችም ተባለች፡፡
ክው ብላ ደነገጠች፡፡ “ምነው? ምን አደረኳት አዜቢናን?” ሽምቅቅ ብላ፤ ስልኩን አስቀምጣ፤ ብቻዋን ጭር ያለ ቦታ ፈልጋ ተቀመጠችና፤ ስቅስቅ ብላ አለቀሰች፡፡ እናቷ የካቲት አስራ ሁለት
ሆስፒታል፣ ወንድሟ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል፣ ምን ዓይነት ስቃይ
ነው? እንደተመኘችው ሳታየው መሸ፡፡ በማግስቱ እናቷን ጠይቃ፤ ወደ
ወንድሟ መጣች፡፡ ልታየው አልቻለችም፡፡ ፀጉሯን እንኳን ማበጠር አቁማለች፡፡ እንደዚያ የምታምረው ልጅ ነገሮች ተደራርበውባት፧ ማስፈራሪያ እየመሰለች ነው፡፡ እንደዚህ ሆና መከራዋን ካየች በኋላ ወንድሟን ያገኘችው፤ በሶስተኛው ቀኑ ነው፡፡
አንዱአለም ድንበሩ ከሞት ድንበር ደርሶ ተመለሰ፡፡ በሶስተኛው ቀን፤ በሶስተኛ ማዕረግ ከቀዶ ጥገና በሽተኞች ጋር ተቀላቀለ፡፡ እንደዚያ ፊቱ አብጦና፤ ጠቁሮ፤ ስታየው የምትሆነውን ነበር ያጣችው፡፡
“አንዱዬ ምንድነው የሆንከው?” ቀስ ብላ ጠየቀችው። ከትንፋሹ
ጋር እየታገለ....
“እንደሻው... አስደበደበኝ” ብሉ ነገራት፡፡ በዚህ ጊዜ የተሰማትን ስሜት መግለጽ ያስቸግራል፡፡ አዜብ የሸሸችበት ሚስጥር አሁን ገና ወለል ብሎ ታያት፡፡ ሰውነቷን የሆነ ነገር ውርር አደረጋት :: እንደሻው
በግንባሩ ላይ ብዙ ጠመዝማዛ ቀንዶች አብቅሎ፣ ጥርሶቹ ተስለውና፤
አንደመጋዝ ሾለው፣ ጥፍሮቹ እንደ ጃርት እሾህ ተንጨፍርረው፣ ታይዋት፡፡ .
እንደሻው ... እንደሻው ... እንደሻው ... አእምሮዋን እንድትስት አድርጉ ከመታት በኋላ ሊከመርባት፤ በሀሳብዋ መጣባት፡፡ ሰውነቷ እንደሻው ምን ያላደረጋት ነገር አለ? የምትወደው ሻምበል ብሩክን ያጣችው በእንደሻው ምክንያት ነው፡፡ ዶክተር ባይከዳኝ እንደዚያ ውሻ አድርጐ የሰደባት፤ በኋላም ስለእናቷ ክፉ ንግግር የተናገራት፤ እንደሻው በፈጸመባት ወንጀል ምክንያት ነው፡፡ ስራዋንም ያጣችው በሱ
ድርጊት የተነሳ ነው፡፡ ለዚህ ሁሉ ግፍ ምንም የበቀል እርምጃ አልወሰደችም፡፡ እሷ ብትተወውም ግን እሱ ሊተዋት አልፈለገም፡፡
ይሄውና አሁን ደግሞ እንደ ዐይኗ ብሌን የምትሳሳለት፤ አንድና ብቸኛ ወንድሟን እንዳይሞት እንዳይድን፣ አድርጉ! አስደበደበው፡፡ ግን ለምን ይሄን ያክል ጨከነባት?
“የሰው ልጅ አይደለሁም እንዴ? ምነው ምን አደረኩት?” በሚል ጭንቀት ተውጣ ራሷን ጠየቀች፡፡ በሷ እምነት ምንም
አላደረገችውም።የፈጸመችበት በደል አልነበረም፡፡ የማፈቅረው ሰው ስላለኝ
ይቅርታ አድርግልኝ ብላ ለምና ተለማምጣ ልታግባባው ሞከረች እንጂ
አንዳችም ክፉ ነገር አልወጣትም፡፡እሱ ግን ያንን እንደ ጥቃት ቆጥሮ፤ በጭካኔ ደብድቦ፧ ክብረ ንጽህናዋን መድፈሩ ሳያንሰው አሁን ደግሞ እንደገና ,በወንድሟ ላይ የጭካኔ በትሩን አሳረፈ፡፡ግን ለምን?... ለምን?...ለምን?... ለዚህ ጥያቄዋ መልሱ ብዙም ሳይቆይ ወደ አእምሮዋ መጣላት፡፡ አላንገራገረችም፡፡ ይሄ የመጨረሻው ምዕራፍ ነው ስትል ወሰነች፡፡ የሆነውን ሁሉ በተቆራረጠ ድምጽ ነገራት፡፡
አሁን ሁሉንም ነገር ሰምታ ከጨረሰች በኋላ አዜብ አሳዘነቻት፡፡ እሷን ጠልታ ሳይሆን፤ በሷ ላይ በተደጋጋሚ ለሚደርሰው አስጠሊታ አጋጣሚ ሁሉ እጂ ስላለበት፤ መጥፎ ስሜት ተሰምቷት እንደሆነ ስታውቅ፤ “ጓደኛዬን አስጨነኳት፡፡ ጭንቀቴ እንጂ አንድም ቀን ደስታዬ
ተርፏት አያውቅም፡፡ በዚያው ለሷም ግልግል ነው፡፡” የሚል ስሜት
አደረባት፡፡

ታሪኩን በሙሉ አንድ በአንድ ሰምታ ስታበቃም፤ አሞቷ ኮስተር አለ፡፡ ለሁሉም ገደብ አለው፡፡ ትዕግሥትም ልክ አለው፡፡ እንኳንስ በደል፤ ማርም ሲበዛ ይመራል። በደል ሲደጋገም ደግሞ ከምሬት በላይ ነው፡፡ በቃ! እንደሻውን ልትበቀለው ስመ እግዚአብሔርን ጠርታ በልቧ መሀላ
ፈጸመች፡፡

አንዱዓለም የምትወደው ታናሽ ወንድሟ፤ የተፈጸመባት ግፍ አንገብግቦት ሊበቀልላት ሄዶ ጉድ ሆኗል፡፡ እሷ ደግሞ በታናሽ ወንድሟ ላይ ለተፈጸመው ወንጀል ምላሽ መስጠት አያቅታትም፡የመጨረሻው የአባቷ ቅርስ ታያት፡፡ በክብር ተሸፍኖ በሣጥን ውስጥ በድብቅ
የተቀመጠውን፣ እሷና እናቷ ብቻ የሚያውቁትን፣ መቶ አለቃ
👍2
ድንበሩ ከጎኑ ሻጥ ያደርገው የነበረውን፤ የአሜሪካ ኩልት ሽጉጥ ከነዝናሩ...
አንዱዓለም ስለዚያ የሚያውቀው ነገር የለም፡፡ እናቷና እሷ የደበቁትም በጉርምስና ስሜት ተነሳስቶ ወንጀል ይፈጽምበታል በሚል ፍራቻ ነው።
ለረጅም ጊዜ ሥራ ፈትቶ የተኛው የአባቷ ሽጉጥ ሥራ ሊያገኝ ነው፡፡ የእንደሻው ገላ በጥይት ተበሳስቶ ወንፊት ሲሆን ታየት፡፡ እሷም ጠላቷን ጥላ በክብር ስትወድቅ ታያት...
ያለውን በሙሉ በሱ ላይ አርከፍክፋ፤ የመጨረሻዋ አንዷን እንደ ኪኒን ለመዋጥ ወሰነች፡፡ ይህንን ቃሏን እንዳለፈው ጊዜ ዳግም ላታጥፈው፣ ከዚህ በኋላ የውርደት ኑሮ ከመኖር ጠላቷን አጥፍታ
በጀግንነት ለመሞት ወስና ውሳኔዋን በፊርማዋ ካፀደቀች በኋላ፤ የሆነ
በራስ የመተማመን ስሜት ተሰማት፡፡ ነገሮች ሁሉ ቅልል ብለው ታይዋት፡፡ የምን ለሆነው ላልሆነው ማልቀስ ነው?! ኑሮ የተባለውስ የትኛው የሚያጓጓ ኑሮ ነው? :: ኑሮ እንደትንኝ ድቅቅ ብላ አንሳና ቀጭጫ ታየቻት፡፡ አሁን ነገሮች ሁሉ የመጨረሻው ደረጃ ላይ መድረሳቸውን አወቀች። ከዚህ ውሳኔዋ ፈቀቅ የሚያደርጋት አንዳችም
ሃይል አይኖርም፡፡ በቃ!!....
“አይዞህ አንዱዬ! እህትህ አለሁልህ! ደምህ እንደዚህ ሜዳ ላይ ፈስሶ አይቀርም!" ቀስ ብላ ሄዳ እዚያ ያበጠ ጉንጩ ላይ ሳም ካደረገችው በኋላ ከሆስፒታሉ ወጥታ በቀጥታ ወደ ቤቷ ሄደች...

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2
አትሮኖስ pinned «#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ ፡ ፡ #ክፍል_ሰላሳ_ሶስት ፡ ፡ #ድርሰት_በትክክል_ገና ..“ይሸጣል እንዴ?” ከመካከላቸው አንዱ፡፡ “አሉልህ እኮ አሁን ወጣ ብለን ብንፈልግ ደማቸውን እንደ ጭማቂ ለመሸጥ የሚንጐራደዱ አይታጡም" ”ሌላው፡፡ ይሄ ደግሞ የገንዘብ መስዋዕትነትን ጠየቀ፡፡ አሁንም ተፋጠጡ፡፡ “አቦ ትጠራ ምን ትሆናለች” ባዩ በዛና ትህትና ይሄንን መርዶ በጠዋቱ እንድትረዳ ፈረዱባት፡፡ ከዚያም ልጁ…»
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሰላሳ_አራት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

#ክፍል_ሁለት
#ቬንዴታ
#ብቀላ

...በፈጸመባት ተደጋጋሚ ወንጀል ምክንያት ህሊናዋ ሊሸከመው
ከሚችለው በላይ በደል ያደረሰባት፤ እንደሻውን አጥፍታ፤ እራሷን ለማጥፋት የገባችውን ቃል ተግባራዊ የምታደርግበት የመጨረሻዋ ሰዓት
ከአክስቷ ጀምሮ የቅርብ የሆኑ ሰዎችን በሙሉ ተዘዋውራ ጠየቀች፡ስንብት መሆኑን አላወቁም፡፡

ውሣኔዋን ተግባራዊ የምታደርገው እንደ ነገ ሆኖ፤ ዛሬ ግን አሉኝ የምትላቸውን እናቷን፣ ወንድሟን፣ ጓደኛዋን፣ በደንብ አጫውታ መለየት አለባትና፤ የልቧን በልቧ ይዛ፤ እንደታላቅ እህቷ የምታየት፣ ደስታዋንም ሆነ ከሁሉም በላይ ችግሯን ስትጋራት የኖረች ጓደኛዋን በፍቅር ልትሰናበታት ሄደች፡፡
እንዳገኘቻት ሄዳ እላይዋ ላይ ጥምጥም ብላ አለቀሰች፡፡ አዜብም እንደሷው አቀፈቻትና ተላቀሱ፡፡
“በፍጹም እንደዚህ ያለ አደጋ ይደርስበታል ብዬ አልገመትኩም ነበር፡፡ ትሁቲና እኔ ባንቺ ምንም ዕድለኛ አልሆንኩም፡፡ የኔ ድርጊትና ምክር ሁል ጊዜ ሲጉዳሽ እንጂ ሲጠቅምሽ ባለማየቴ፤ በጣም ነው
የተሰማኝ፡፡ ከዚህ ሁሉ ለምን ትንሽ ራቅ አልልላትም የሚል ስሜት ተሰምቶኝ ነው እንጂ፣አንቺን ለማሳዘን አይደለም፡፡ ይቅርታ አድርጊልኝ” በማለት እየሳመች፤ እያባበለች፤ ይቅርታ ለመነቻት፡፡
“አዜቢና ቁጭት ተሰምቶሽ ነገርሽው እንጂ፤ እንደዚህ ጭካኔ የተሞላበት የከፋ ጉዳት ያደርስበታል ብለሽ እንዳላሰብሽ ይገባኛል። በዚህ ምንም ልትፀፀቺ አይገባም፡፡ እግዚአብሔር ገና ስፈጠር ይህንን ሁሉ መከራ እንድሸከም ፈርዶብኝ ያሸከመኝ እዳ ስለሆነ እችለዋለሁ :: አንቺ
ግን ሁሌም ስቸገር ከጉኔ ከመገኘት ሌላ ምንም ያደረግሽኝ ነገር ስለሌለ
መጥፎ ስሜት በፍጹም ሊሰማሽ አይገባም፡፡ እንኳንም ብቻ ከሞት
ተረፈ፡፡ ምንም ቅሬታ አላደረብኝም፡፡ አትጨነቂ የኔ ቆንጆ፡፡ ብላ እቅፍ አድርጋ አፅናናቻትና፤ እንደ ዱሮአቸው በፍቅር ሲጨዋወቱ አረፈዱ፡፡ለሻምበል ብሩክ ስልክ ደውላ አንዱአለም ስለደረሰበት አደጋ የነገረችው መሆኑን፤ እሱም ደንግጦ "አይዞሽ እንደሻውን ገርፈን እናውጣጣዋለን" በማለት ቃል የገባላት መሆኑን፤ እውነት አስመስላ ስትነግራት አዜብ ተደሰተች፡፡ እንደሻው የእጁን እንዲያገኝ ቸኮለች፡፡

“በጣም ቆንጆ ነው ያደረግሽው ትሁትዬ የውስጥ እግሩ ወደ ውጭ እስኪገለበጥ ድረስ እንዲያስገርፈው አድርጊ፡፡ ይሄ ግፈኛ! ለሱ ምንም ምህረት አያስፈልገውም!” ስትል በቁጭት መከረቻት፡፡ ነገ ጠዋት በፓሊስ እንደሚያስወስድላትና! የሚሰራበትን ሱቅ
ለመጠቆም፡ ዛሬ ቦታውን ማየት እንደሚያስፈልጋት ስትነግራት፤ አዜብ
ልብሷን ቶሎ ለባብሳ ተነሳች፡፡መርካቶ ሄደው የእንደሻውን ሱቅ በሩቁ አሳየቻት፡፡ ሱቁን በስንት ሰዓት እንደሚከፍት ሁሉ በቂ መረጃ አገኘች፡፡ ዋናው
የእንደሻውን ሱቅ ማየቱ ነበር፡፡

ዓላማዋ እንደሻው ውስጡ ይንጐራደዳል፡፡ ለነገው ብቀላ እንድ እርምጃ ተጠናቀቀ፡፡ እዚያ ሱቅ ውስጥ ነገ... ነገ... ጠዋት ጠላቷ ገላው፣
በጥይት ወንፊት ሆኖ የወንድሟን ደም እንዳንዠቀዠቀው፣ ደሙ ይንዠቀዠቃል....

ይህንን የነገውን ትርዒት በአእምሮዋ እያውጠነጠነች፤ ተያይዘው ወደ እነ አዜብ ቤት ተመለሱ፡፡
በመሰነባበቻቸው ሰዓት ላይ ግን የትህትና ሁኔታ ትንሽ ከወትሮው ለየት አለ፡፡ ጥብቅ አድርጋ አቀፈቻት፡፡ እያገላበጠች ሳመቻት፡፡ እንደገና ... እንደገና ... እንደገና ይህ ለአዜብ እንግዳ ነበር፡፡ ትህትና
ግን የስንብት ስለሆነ አልታወቃትም፡፡

ዐይኖቿ ፍዝዝ ብለው፤ እላይዋ ላይ ተተክለው ይቀሩ ነበር፡፡ እነዚያ ውብ ዐይኖቿ፣ ለየት ያለ መልዕክት ያስተላልፉ ነበር፡፡ ስንብት! ደህና ሁኝልኝ ውዷ ጓደኛዬ.... ዐይነት፡፡ አሁን ደግሞ ትንፋሽ
እስከሚያጥራት ድረስ አቅፋ እየተሰናበተቻት ነው፡፡ይህ የትህትና ሁኔታ
አዜብን ረበሻት፡፡
“ስላስቀየምኳት ይሆን ወይስ?...” መልስ የሌለው ጥያቄ፡፡ በመጨረሻም አገላብጣ ሳመቻትና፤ ታክሲ ውስጥ ገባች። ዞር ብላ
እጆቿን አውለበለበችላት፡፡ የምሣ ሰዓት ደርሶ ነበር፡፡ ምሣ በሁለት ሣህን
አዘጋጅታ፣ ሠራተኛዋ የካቲት አሥራ ሁለት ሆስፒታል እናቷ ጋ እንድትሄድ ስታደርግ፤ እሷ ደግሞ ወደ ወንድሟ ሄደች፡፡ ሆስፒታል ውስጥ ወንድሟን ስታጨዋውተው ዋለች፡፡ አዳሯን ደግሞ እናቷ ጋ አስባለች፡፡
የቀኑን ፕሮግራም ሙሉ ለሙሉ ለአንዱዓለም ሰጠችው፡፡ወንድሟን ለመሰናበት ስሜቷን በእንባ ለመግለጽ አልፈለገችም፡፡ ሆዷ እንዳይባባ፤ ራሷን አጠነከረች፡፡ በእርግጥም ተሳካላት፡፡ ከምንጊዜውም የበለጠ ሳቂታና ደስተኛ መስላ ታየች፡፡

እዚያ አጠገቡ ቁጭ ብላ እንዲሁ ስትደባብሰው፣ ስታሻሽው፣ ስትስመው፣ ስታሳስቀው፤ ዋለች፡፡ ሰዓቱ እየሄደ ነው፡፡ የምታዘጋጀው ደብዳቤ አለ፡፡ እናቷ ዘንድ አዳሪ ነች፡፡ ልትለየው ባትፈልግም ፤ ጣጣዋ ብዙ ነውና፤ ልትሰናበተው ተዘጋጀች፡፡

በዚያን ሰዓት ግን ቆራጥ የነበረችው ልጅ ተረታች፡፡ ሳታስበው እላዩ ላይ ድፍት እንዳለች ቀረች፡፡ ሆዷ ቡጭ ቡጭ አለ፡፡ መተንፈስ አስከሚያቅተው ደረስ እላዩ ላይ ተጣበቀች፡፡
በሽተኛ መሆኑን ዘንግታ፤ አየር አሳጠረችው፡፡ እንዱዓለም ቶሎ
ቶሎ መተንፈስ ሲጀምር፤ ደንግጣ ቀና አለችለት፡፡ በዚያን ጊዜ ግን ዕይኖቿ በእንባ ተሞልተው ነበረና፤ እንባዋ እየወረደ ፊቱን አረጠበው፡፡
“ተሽሎኛል እኮ እታለምዬ ለምን ታለቅሻለሽ?” ለመጨረሻ ጊዜ እንደምትሰናበተው ያላወቀው ወንድሟ፡፡ እየደጋገመች ሳመችው፡፡ “ደህና
ሁንልኝ አንዱዓለሜ” ከሳግ ጋር እየተናነቀች ተነሣች፡፡
“ደህና እደሪ እታለም” በአለቃቀሷ ሆዱን ባር ባር እያለው፡፡ ከዚያም ወደ ኋላ ገልመጥ አለችና ባይ ባይ " በማለት እጆቿን አወዛወዘችለት፡፡ የመጨረሻ ስንብት፡፡ ከዚያም በሚንከራተቱት ዐይኖቿ
በስስት ተሰናበተችውና፤ ፈጠን ብላ ክፍሉን ለቃ ወጣች፡፡

እቤት እንደደረሰች ለሻምበል ብሩክ ደብዳቤ ትጽፍ ጀመር፡፡
“ይድረስ ለማፈቅርህ ውድ ወንድሜ ለሻምበል ብሩክ በላይ ለጤናህ እንደምን አለህልኝ፡፡ እኔ እግዚአብሔር ይመስገን በጣም ደህና ነኝ፡፡ ብሩኬ በጣም ናፍቀኸኛል፡፡ ግን ምን ያደርጋል? አልታደልኩምና ናፍቆቴን መወጣት አልችልም፡፡ይህ የመጨረሻው ቃሌ ስለሆነ አንድ ነገር ልጠይቅህ? ይህንን ደብዳቤ አንብበህ ከመጨረስህ በፊት እንዳታቋርጠው እሺ? ዛሬ የምንግርህ በሙሉ ቁም ነገር ነው እሺ? ብሩኬ መጀመሪያ ያየሁህ ዕለት የደነገጥኩብህ እኮ አባዬን ስለመሰልከኝ ነበር፡፡ አባዬ ልክ እንዳንተው እንዴት መሰለህ የሚያምረው? በተለይ የምትለብሱት
ዩኒፎርም እንዴት መሰለህ የሚያምርባችሁ። በቁመታችሁ፣ በግርማ
ሞገሳችሁ፣ በቃ ምን ልበልህ አንድ ዐይነት ናችሁ፡፡ ያኔኮ ጣቢያ መጥቼ
ቢሮህ ስገባ ደንግጬ የቀረሁት ለዚያ ነበረ፡፡ ምናልባትም የዚያን ዕለት
የተሰማኝ ስሜት በህይወቴ ውስጥ የመጀመሪያው ነበረ ብልህ ውሸታም
አድርገህ ስለቆጠርከኝ አታምነኝ ይሆናል፡፡ እንደዚያ ለወንድ ልጅ
ደንግጬ አላውቅም ነበረ፡፡ ባንተ ግን ደነገጥኩ፡፡ ከዚያም ቀስ በቀስ ወደድኩህ፡፡ ቀንም ሆነ ሌሊት አስብህ ጀመር፡፡ ስላንት ማውራት ደስ ይለኛል፡፡ እንደዚያ የሚያደርገኝ አዲስ ነገር ፍቅር መሆኑን ከኔ በፊት ያወቀችው አዜብ ነች ብልህ ይገርምህ ይሆናል፡፡ ብሩኬ ሙት አሁንም እወድሀለሁ፡፡ በእውነት እኔ እኮ ባለጌ ልጅ አልነበርኩም፡፡ የሆነውን ሁሉ
ልንገርህ? ዶክተር ባይከዳኝ ምኔም አይደለም፡፡ ምንም አላደረገኝም፡፡ ከሱ
ጋር የነበረኝ ግንኙነት እናቴን አክሞ እንዲያድንልኝ እንጂ ባንተ ላይ
ደርቤ ያፈቀረኩት ሰው ሆኖ አልነበረም አንተ ከዶክተር ባይከዳኝ
👍3
ጋር ሆኜ ባየኸኝ ወቅት ላይ እንደሻው ከአበራ ጋር ተመሳጥረው ምን እንዳደረጉኝ ዝርዝሩን አዜቢና ትነግርሃለች፡፡ እሷ ሁሉንም ነገር ታውቀዋለች፡፡ ብሩኬ እኔኮ ሸርሙጣ አይደለሁም? ዶክተር ባይከዳኝ ግን
እንደዚያ ብሎ ሰደበኝ፡፡ እማዬም በጡት ካንሰር በሽታ መታመሟንና የማትድን መሆኗን በጭካኔ ነገረኝ፡፡ የምሰቃየው እኮ እሷ እንድትድንልኝ ነበረ፡፡ ከሷ ቀጥሎ አንዱዓለሜንና አንተን ነጥዬ አላያችሁም አንተንም አጣሁህ፡፡ አንተን ያጣሁህ እንደሻው አስገድዶ ክብረ ንጽህናዬን
በመድፈር፤ በፈጸመብኝ ወንጀል ምክንያት ነው፡፡ አንዱዬ እንደሻው ምን እንዳደረገኝ ከአዜብ ሰምቶ ሄዶ ቢያነጋግረው፤ እንዳይሞት እንዳይድን አድርጎ አስደብድቦት፤ አሁን ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ገብቷል፡፡እንደሻው በዓለም ላይ አሉኝ የምላቸውን ሁሉ እንዳጣ ያላደረገው ጥረት የለም፡፡ ግፍ ሠራብኝ ብዬ ግን አልተከታተልኩም ነበረ፡፡ ብተወው
አልተውሽ አለኝ፡፡ ሴት ነች፡፡ ምን እባቷ ታደርገኛለች ብሎ ነው አይደለም? እኔ ግን እሱ እንደገመተኝ ፈሪ አይደለሁም፡፡ የወታደር ልጅ ነኝ እኮ፡፡ አባዬ የአገር ጥቃት ሊከላከል ሄዶ አይደል የቀረው? እኔ ሴቷ ልጁ ደግሞ የወንድሜንና የራሴን ጥቃት መከላከል ያቅተኛል? አያቅተኝም፡፡ ቢያንስ፤ ቢያንስ፤ እንደዚህ እንደ አሁኑ ገድሎ መሞት አያቅተኝም፡፡ ከዚህ በኋላ ያለው ህይወቴ እኮ ጨለማ ነው፡፡ እናቴ
አትድንም፡፡ የማፈቅርህ ጓደኛዬ አንተንም አጥቼሃለሁ። እንዱዓለሜ ተጉድቷል፡፡ ታዲያ ይህንን ሁሉ ስቃይ ተሸክሞ ያለ አባት ከመኖር መሞት አይሻልም? ብሩኬ ሙት በጣም ይሻላል እግዚአብሔር ለምን በዚህ ሁሉ ቅጣት ሊቀጣኝ እንደፈለገ ሳስበው አንዳንዴ ይገርመኝና፤ መኖሩንም ያጠራጥረኛል፡፡ አሁን ግን አግዚአብሔርን የምወቅስበት፣ ወይንም መኖሩን የምጠራጠርበት ጊዜ አይደለም፡፡ በደሌን ይቅር እንዲለኝ የምለምንበት ጊዜ ነው፡፡ ብሩኬ እኔን አላመንከኝም አይደል? አዜቢናን ግን ስለሁሉም ነገር ጠይቃት፡፡ እሷ ሁሉንም ነገር አንድ በአንድ ታስረዳሃለች፡፡ የነገርኩህ ሁሉ እውነት ልብወለድ ያለመሆኑን፤ ታረጋግጥልሀለች፡፡ ብሩኬ ካለኔ ተስፋ የሌላቸውን መሆኑን፤
እንዱዓለሜንና እማዬን ሆስፒታል ሄደህ ዐይናቸውን እይልኝ እሺ?
ብትችል ሆስፒታል ውስጥ ከመሞቷ በፊት ቤቷ ገብታ እንድትሞትና የመቃብሯን ሳጥን አደራ ልበልህ ?፡ የዚያን ጊዜ እሪ! ብዬ ያለቀስኩት ደግሞ ለምን እንደሆነ አዜብ ትነግርሃለች፡፡ በቃ እንዳላጣህ ነበር፡፡ነገር ከሆነ በኋላ እንዳጣህ አልፈለግሁም፡፡ ፈራሁ፡፡ የምታምነኝ ስላልመሰለኝ ፈራሁ እውነቱን
አዜብ ጋር ተመካከርንና እንደሱ እንዳደርግ ተስማማንበት፡፡ በህይወቴ
የማስታውስው የሰራሁት ትልቁ ሀጢአት ቢኖር እሱ ይመሰለኛል፡፡ ባንተ
ላይ እንደዚያ አይነት ስራ ከምስራ! እውነቱን ነግሬህ እንደ ዶክትር
አዋርደህ፤ ብታባርረኝ ይሻለኝ ነበረ፡፡ አንተን ማስቀየም በጣም ከባድ ነገር ነው እንደዚያም ሆኖ ግን አልተሳካልኝም፡፡
ከሽፈ፡፡ ነገሩ ሁሉ አሳዛኝ ሆነ፡፡ አንድ ነገር ልንገርህ ብሩኬ? ከሁሉ የሚበልጠው ክብረ ህሊና እንጂ ክብረ ንጽህና እንደሻውን በመሰለ ጨካኝ ሰውም ሊጠፋ የሚችል ስለሆነ፤ ትልቅ ግምት አትስጠው እሺ?፡፡ ዋናው ፍቅር ነው፡፡ በመጨረሻ ላይ አደራ የምልህ አንድ ነገር አለ፡፡ የሁለታችን እህል ውሃ ሊያበቃ ሰሞን፤ በህልሜ አብረን በመናፈሻ ውስጥ
ስንንሸራሽር፤ የሰጠኸኝ ጽጌረዳ እጄ ላይ ደርቃ አየሁ፡፡ እውነትም ህልሜ እውን ሆነ፡፡ ፍቅራችን ደረቀ፡፡ አሁን አደራ የምልህ በመቃብሬ ላይ እሷን የምትመስል አንድ ጽጌረዳ እንድትተክልልኝ ነው ።እሺ ብሩኬ? ነፍሴ
በሷ እንኳን ትለምልም እስቲ፡፡ ብሩኬ ልለይህ ነው፡፡ አሁን ሁሉም ነገር
አብቅቷል፡፡ በወሰድኩት እርምጃ ደግሞ ምንም ዐይነት ፀፀት እንዳይሰማህ
እሺ ?፡፡ ብሩኬ አንተ እኮ ወርቅ ሰው ነህ፡ ምንም አልበደልከኝም፡፡ እንደ ዶክተር ባይከዳኝ ሞራሌን ነክተህ አዋርደህ አላባረርከኝም፡፡ አጽናንተህ፤ አባብለህ፤ ነው የሸኘኝ :: ስለዚህ ምንም አይነት ጸጸት ሊያድርብህ አይገባም፡፡ በልጅነቴ የማውቀው አቢላዛር ምንም በማያውቀው ነገር አባቱ ለስቃይ እንደዳረገው ሁሉ፤ አንተ በማታውቀው፤ እኔም በደረሰብኝ መጥፎ አጋጣሚና ምክንያት፤ ህይወቴ ለስቃይ ተዳረገች እንጂ፤ እኔና አንተ ሳንግባባ ቀርተን የተፈጠረ ችግር ባለመኖሩ፤ በእኔ እምነት
ሁለታችንም በደለኞች አይደለንም ብሩኬ ይህ ደብዳቤ በሚደርስህ ስዓት
እርግጠኛ ነኝ ሁሉም ነገር አብቅቶ ታገኘዋለህ፡፡ መርካቶ ገበያ አዳራሽ
አካባቢ፤ ጠላቴን እንደሻውን ጥዬ ወድቄአለሁ፡፡ ለአዜቢና በ97 11 11
ደውለህ ንገራት፡፡ ብሩኬ እውድሃለሁ፡፡ ለፍቅር የመጀመሪያዬም፣ የመጨረሻዬም አንተው ብቻ እንደነበርክ በዚች በመጨረሻዋ ሰአት እንኳ ልብህ ሙሉ በሙሉ አምኖ እንዲቀበለኝ እለምንሃለሁ፡፡ ብሩኬ በቀሪው ዘመንህ መልካሙ
እንዲገጥምህ ነፍሴ ትመኝልሃለች ወንድሞችህን ተሰናበትልኝ፡፡ ደህና ሁንልኝ፡፡
እስከወዲያኛው አፍቃሪ እህትህ ትህትና ድንበሩ፡፡ ደብዳቤውን ጽፋ ካበቃች በኋላ መኝታ ክፍሏ ውስጥ ገባችና ቆለፈችው
በሩን ከዚያም ሽጉጡን ከማኀደሩ አወጣችና፤ በሚገባ ወለወለችው፡፡
ውስጡ የነበሩትን ጥይቶች አውጥታ ወደ
ጎን ካስቀመጠች በኋላ ፤ ከዝናሩ ላይ እየለቀመች አዲስ አዲስ የመሰሏትን
ስድስት ጥይቶች ለየች ፡፡ ከዚያም ሽጉጡን ባዶውን ቀጭ ቋ ! ቀጭ
እያደረገች ደጋግማ ምላጩን ሳበች፡፡
ሽጉጡን ዘቅዝቃ! ጥይቶቹ የሚገቡበትን ቀዳዳዎቹን አፀዳዳችና አሁንም ደጋግማ ሳበችው፡፡ቀጭ! ቀጭ! ቀጭ! እያለ የጥይት አቃፊው ተሽከረከረ፡፡ ከዚያም
ጥይቶቹን ሙሉ ለሙሉ አጉርሳ ስታበቃ፤ ሽጉጡን በቀኝ እጇ ይዛ፤ ፊት ለፊት ደቀነችና፤ ግራ ዓይኗን ጨፍና፤ አነጣጠረች በጠላቷ ላይ...
በመጨረሻም ቀስ ብላ መጠበቂያውን አጠበቀችና፤ በጨርቅ ከጠቀለለችው
በኋላ፤ በእጅ ቦርሣዋ ውስጥ አስቀመጠችው፡፡
አሁን ከምሽቱ አሥራ ሁለት ሰዓት ሆኗል፡፡ መጀመሪያ ለሻምበል ብሩክ የጻፈችለትን ደብዳቤ መሥሪያ ቤቱ ልታደርስ፣ ከዚያም
በኋላ እናቷጋ አድራ በጠዋት ወደ መርካቶ ለመሄድ አቀደች፡፡
ከቀኑ አሥራ ሁለት ሰዓት ተኩል ሆኗል፡፡ ሻምበል ብሩክ ከሥራ ወጥቶ ወደ ቤቱ ሄዷል፡፡ ያለመኖሩን ካረጋገጠች በኋላ፤
ተረኛውን ፖሊስ አነጋገረችው፡፡
ከክፍለ ሀገር የመጣች ዘመዱ መሆኗን አስረዳችና፤ ጠዋት ሥራ ሲገባ ፓስታውን እንዲሰጥላት ጠየቀችው፡፡
“እሺ የኔ ቆንጆ ጠዋት እንደገባ እስጥልሻለሁ” አላት፡፡
“አደራ” አለችው፡፡
“ኧረ ችግር የለም እንኳን የሻምበል ብሩክን የሌላም መልዕክት እናደርሳለን፡፡ ግድ የለሽም አይመቸኝም አልሽ እንጂ፤ ጠዋት ብትመጪ ታገኝው ነበር” አላት፡፡
“እንደገባ ይስጡልኝ፡፡ እንዳይረሱት” በማለት አደራዋን ጠበቅ አድርጋ፤ ከፓስታው ላይ “ለሻምበል ብሩክ በላይ በእጅ የሚሰጥ የአደራ ደብዳቤ” የሚል ጻፈችበት፡፡
ፖሊሱ ተቀበላትና፤ ደብዳቤውን ከኪሱ አኖረው፡፡ “ እግዜር ይስጥልኝ” በማለት ከወዲሁ ምስጋናዋን አቅርባ፤ ለመጨረሻ ጊዜ የምትሰናበታት እናቷ ዘንድ ለማደር፤ ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ሄደች፡፡
እናቷን አቅፋ ስማ፤ እህል አቅምሳት፤ አጠገቧ ሆና፤ የሆነ ያልሆነውን ስታወራላት፤ አመሸች፡፡
“አንዱዓለሜስ ምነው ብቅ አላለ?” ስትል ጠየቀቻት፡፡ ፈተና ስለደረሰበት ከጓደኞቹ ጋር ይህችን ሰሞን ጠንክሮ እያጠና መሆኑን ነገረቻት፡፡
“ይሁን ይበርታ” ብላ! እንዲቀናው ከልቧ ተመኝታ፤ ከሴት ልጇ ጋር በሰፊው ሲጫወቱ አመሹ፡፡.....

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍3
#ሰመመን


#ክፍል_አርባ_ዘጠኝ


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

ከገና ማዕበል ያመለጠው ተማሪ፥ የዩኒቨርስቲ ውስጥ ዕድሜው መራዘሙን ካረጋገጠ በኋላ መረጋጋት ይታይበታል ። የሁለተኛው ሴሚስተር ትምህርት ቢጀመርም ገና ሞቅ ሞቅ ባለማለቱ አንገቱን መልሶ ቀለም ላይ የደፋ ተማሪ
እምብዛ!” ነው ። ሆኖም ፋታ ፈጥሮአቸው የነበሩት ቀልድ ፥ትችት።ውንጀላና ተረብ ተግ ብለዋል ።

ትዕግሥት ማጥናት አልጀመረችም ። የወረቀት ዘር ማየት ያስጠላት ትመስላለች ትምህርት ክፍሉ ውስጥ እንኳ ከመምህራኑ ገለጻ ሙሉ በሙሉ ማስታወሻ መውሰዷን ትጠራጠራለች ። ምክንያቱ አንዳንዴ ሐሳቧ እያመለጣት
ወደ ወጭ መብረር ጀምሯል ፤ በግልጽ ያልተከተላት ስሜት ሲፈታተናት ይሰማታል ከውስጧ አንዳች ነገር የጎደለ ይመስላታል። ምናልባት በቢልልኝ አገላለጽ ለፍቅር የተዘጋጀው ሥፍራ ሳይሆን አይቀርም የሚረብሻት ።

እቤል ሕመሙን አጋብቶባት እንደ ሄደ ለመገመት ብዙ ጊዜ አልወሰደባትም ። መኝታ ክፍሏ መግባት መውጣትም አስጠልቷታል ። ጸባይዋ ቢንቋሸሽም ፡ በመጠኑ ለምዳት የነበረችው ጓደኛዋ ማርታ ነበረች ። እሷ ከተባረረች ወዲህ በደንብ ቀርባ የምትጫወተውን የሴት ጓደኛ አላገኘችም ። ከቤተልሔም ጋር ዐልፎ ህልፎ ይገናኛሉ ። ሆኖም በግቢው ውስጥ የቤተልሔም ስም እየቆሸሽ ስለ መጣ ትዕግሥት አብራ እንዳትታማ በመፍራት ቀስ በቀስ እየራቀቻት
ነበር ። አቤል ግቢውን ለቅቆ ከወጣ ወዲህ ለዐይኗ ማሳረፊያ ያገኘችው ሰው እስክንድር ነው ፡ ሳታየዉ ወይም
አግኝታው የተለመደውን “ ታዲያስ ፥ ታዲያስ ” ሰላምታ ሳትለዋወጥ ውላ
አታውቅም ።

እስክንድርም ቢሆን፥የትዕግሥትን መግቢያና መውጪያ ሰዓት ጠብቆ ነው የሚገኛት ፥ ከመኝታ ክፍሉ ጠዋት
ሲወጣ ስለ አቤል ሁኔታ ፍርጥርጥ አርጎ አጫውቷት መፍትሔውን እንዲወያዩበት ሊለምናት ያስብና ፡ በሚያገኛት ጊዜ ልቡ ይከዳዋል ። በዮናታን ፊት የፎከረውንና እሷን ሲያገኛት ምላሱ መተሳስሩን ሲያመዛዝን ራሱን ታዘበው ።
“ አቤልስ ቢደነግጥላትም ቢፈራትም ወዷት ነው ፤እኔ ደግሞ ያሰብኩትን ልነግራት መፍራቴ ለምንድን ነው ? ” እያለ
ከራሱ ጋር መሟገቱ አልቀረም ። ግን ለእስክንድር አልታወቀውም እንጂ፥ ስለ አቤል ጠልቆ ሳያነሳባት ከትዕግሥት ጋር
ግንኙነቱን ማጠናከሩ ለዓላማው ጥሩ መንገድ አመቻችቶለት ነበር ። በአንዴ ነጥቡ ላይ ደርሶ ዱብ ዕዳ ከማውረድ ፥ ቀስ በቀስ አለማምዶ ከነጥቡ ላይ መድረሱን መልሱ የእሽታ እንዲሆን ይበልጥ ይረዳል ።

ትዕግሥትን ከአቤል ጋር ለማገናኘት አማራጭ መንገዶችን ዮናታንና ቢልልኝ ተነጋግረው ነበር ። ትዕግሥትን ድንገት ወስዶ አቤል ፊት ማቅረቡን ቢልልኝ አልደገፉትም ምናልባትም ካለፈው ልምዳቸው በመነሣት ሊሆን ይችላል።
አንዴ እንዲሁ ተመሳሳይ ችግር የገጠመው ተማሪ የሚፈልጋትን ልጅ አቅርበው እናስተዋውቅህ ሲሉት፡ ካልገደልኳት ብሎ የተጋበዘው ነገር ምንጊዜም አይረሳቸውም ። እና አሁን ያቀረቡት ሐሳብ በመጀመሪያ አቤል ስለ ትዕግሥት ቀና አመለካከት እንዲኖረው መኮትኮትና አጠገቡ ከመድረሷ በፊት በስልክ እንድታነጋግረው ወይም ደብዳቤ እንድትጽፍለት ማድረግ ነበር ። ደብዳቤ መጻፍዋ የተሻለ መንገድ ሆኖ ተመረጠ ። ይህን ለማስፈጸም በሙሉ ልብ ኃላፊነቱን
የወሰደው እስክንድር ነበር ። ታዲያ አሁን ተግባሩ ላይ ሲዲርስ የምን ወገቤን ያዙኝ ነው ?

ሲያምጥ ከርሞ፡አንድ ቀን እንደ ምንም ደፍሮ ሔደ ። ከመኝታ ክፍሏ አስጠራትና ፡ “ ለጥብቅ ጉዳይ እፈልግሻለሁ ” አላት ። በቆይታ የሚያወሩበት ቦታም ችግር ነበር
እነትዕግሥት ቀድሞ ያጠኑበት የነበረው ከዋናው ቤተ መጹሕፍት ጀርባ ያለው ዋርካ አካባቢ ታየው ። ግን ሁለታችንን
ብቻ እዚያ ዋርካ ሥር ሲያዩን ተማሪዎች ምን ይሉናል ? የሚል ሥጋት እደረበት በመጨረሻም ካወጣ ካወረደ በኋላ ሌላ ቦታ በማጣቱ “ ያሉትን ይበሉ ወደ
ዋርካው ሥር ይዟት ሔደ
እንዴት እንደሚጀምርላት ግራ ገብቶት ትንሽ ተጨነቀ። ግን ዝም ማለትም አልቻለም ። ዐይኖችዋ ውስጥ የጥያቄ
ምልክቶች ተደርድረው ያየ መሰለው ።

“ ሁለታችንም ሳንጠላው የምንሸሸው አርዕስት ነው አላት በድንገት ።

“ ምን ? ” አለችው ፥ ነገሩ ቢገባትም ከእሱው ይምጣ በሚል ስሜት ።

የእቤልን ነገር ሁለቱ በተገናኙ ቁጥር ዳር ዳር ሳይሉ ስለማይለያዩ አሁን ስለእሱ ሊያወራት መሆኑን ትዕግሥት አላጣቸውም ። ስሜቷን ደብቃ ነው እንጂ ወሬውን ለመስ ማት ቸኩላለች

ስለ አቤል በደንብ ላጫውትሽ ብዬ ነው ?” አላት ።

ፈቃደኛነቷን በአፏ ሳይሆን በዐይኖቿ ነው የግለጸችለት ።

አጫወታት ነው ረበሻት የሚባለው ? የለም ! ማጫወት ላይ ላዩን ሲሆን ነው ። ከሥር ከመሠረቱ ጀምሮ ልብን እያናጉ
መንፈስን እያወራጩ ፥ ቁስልን እየቀሰቀሱ ስሜትን እያንገላቱ የሚናገሩት ነገር፡ “ መረበሽ ” የሚለውን ቃል ቢይዝ ይሻላል ። እስክንድር እንደዚያ ነው ያደረገው ። ሳያስበው የእሱም ስሜት አርዕስተ ነገሩ ውስጥ ሰምጦ እየተንገላታ ስለ አቤል የሚያውቀውን ሁሉ ነገራት። እሷን ካየበት
ዕለት ጀምሮ በግሉ የተቀበለውን ሥቃይ አሁን የት እና በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ዘረዘረላት እያወራላት ገጽታዋን ገመገመ ከንፈሯ በቅጽበት ሲከስል ታየው ። ፊቷ በአንዴ ጠወለገ ። አዲስ ነገር ተናግሮ
አልረበሻትም ። አብዛኛው የምታውቀው ነገር ነው ። አብዛኛው ከአቤል ጋር አንድ ሴሚስተር ሙሉ በዐይናቸው የተለዋወጡት የጥናት ፥ የቁጣ ፥ የሥቃይና የእልህ ድምፅ አልባ
ግንኙነት ነው።

“ ታዲያ ጥፋተኛው ማነው ? ” አለችው ንግግሩን መጨረሱን ካረጋገጠች በኋላ
ዐይኖችዋ ያቀረሩትን ዕንባ ሲያይ ስሜትዋ ተጋባበት።ግን እሱ የማልቀስ ችግር አለበት ፤ዕንባው ቶሎ አይመጣለትም ።

ለፍርድ አስቸጋሪ ነው ። ሁለታችሁም ጥፋተኛች አይደላችሁም ። እየተፈላለጉ መራራቅን ፡ “ የፍቅር እንቆቅልሽ ” ብንለው ይሻላል ” አላት ።ዝም አለችው ። እሱም ዝም ብሎ ተመልከታት ። የአቤልን ስሜት ያደነዘዘውን የመልኳን ውበት ማጥናት ፈለገ ።ግን ከዳመነ ፊቷ ላይ ውበት ለማጥናት መሞከሩ አስቸጋሪ
ሆነበት ።

በረዥሙ ተነፈሰች የጭንቅ አተነፋፈስ ። የታባቱ !በሥቃይ የታመቀው አየር ወጣ ።

“ አሁን አንገብጋቢው “ ጥያቄ ጥፋተኛው ማነው?”ሳይሆን ፥ “ መፍትሔው ምንድነው ?” ይመስለኛል” አላት እስክንድር ።

“ ምን መፍትሔ አለው ? ” አለችው ፡ ተስፋ በቆረጠ ድምፅ።

“ አለው እንጂ ።አቤል ይወድሻል ፥ ይፈልግሻል ማወቅ የሚፈልገው ያንቺ ምላሽ ምን እንደሆን ነው ። ካንቺ
መረዳት እንደ ቻልኩት ደግሞ አንቺም ትፈልጊዋለሽ ፤ትወጂዋለሽ ። ይህን ስሜትሽን በደብዳቤ ብትገልጪለት
ችግሩ ይቃለላል ። ”

ደብዳቤ ”አለችው ; ሳይተዋወቁ የምትጽፍለት ደብዳቤ ምን እንደሚሆን ግር ብሏት ።

"አዎ ደብዳቤ !"

"ምን ብዬ ?"
“ በቃ ለእሱ ያለሽን ስሜት ነዋ ! ”

አሰበች ፤ደብዳቤ ። አዎ ጥሩ መንገድ ነው ስትጽፍ አጠገቧ የምታፍረው ወይም የምትፈራው አቤል አይኖርም ወረቀቱ ሳይ የምታሰፍራቸው ቃላት ፈንቅለዋት ማልቀስ ቢዳዳትም ማልቀስ ትችላለች ። ታዛቢ አይኖርባትም ። የምትጽፈው ነገር ከጭንቅላቷ ውስጥ እየፈለቀ ኣሁን አሁን
አሰኛት ።

“ ካልሆነም ረቂቁን እኔ ልጻፍልሽ ” አላት እስክንድር፡ ዝም ስትልበት ጊዜ የቸገራት መስሎት ።

ግድ የለም ፤ እኔው እሞክራለሁ ” አለችው ፥ በሐሳቧ የምትጽፍበትን ቦታ እየመረጠች ምቹ ቦታ የለም ።
የመኝታ ክፍል ጓደኞቿ ከተኙ በኋላ፥ ሌሊት ተነሥታ የመጻፍ ሐሳብ መጣላት ።

“ ጥሩ እንግዲህ ፥ ጸፊና ሰጪኝ ። እኔ አደርስልሻ
ለሁ አላት ። ፈገግ ብላ በእሺታ ራሷን ነቀነቀች ።

እስክንድር በልቡ እየቦረቀ ትዕግሥትን መኝታ ክፍሏ ድረስ ሸኛት ። ምን ዐይነት ደብዳቤ እንደምትጽፍ ለማወቅ ልቡ ክፉኛ ጓጓ ። “ በፖስታ ታሽገው ይሆን ? ” አለ አቤል ጋ ከማድረሱ በፊት ለማንበብ አስቦ ።

ትዕግሥትን ሸኝቶ ሲመለስ ከሩቅ ስሙን የምትጠራ ሴት ሰማ ። ከመኝታ ክፍሏ መስኮት በኩል አይታው የጠራችው ቤተልሔም ነበረች ። ዘወር ብሎ ሽቅብ አያትና ለሰላምታ የጠራችው መስሎት እጁን አውለበለበ “ ቆየኝ ፡ እፈልግሃለሁ ! ” አለችው ።

ለምን ይሆን የፈለገችኝ ? ” ብሎ አሰበ ። መከረኛ ልቡ ያለ ምክንያት ሲነጥር ትሰማው ።

ፎቁን ወርዳ ድክ ድክ እያለች አጠገቡ እስክትደርስ ቆሞ ጠበቃት ።

“ ኡ ... ፍ ! ያደክማል ” አለች አጠገቡ ስትደርስ ተራራ የወጣች ያህል ቶሎ ቶሎ እየተነፈሰች በነጠላ ጫማ ስለ ነበረች፡ከእጥረቷ ጋር በማይጣጥመው ውፍረቷ ይብሱን ቁልቁል ተቀብራበት አጭር በርሜል መሰለችው ። በገጽታዋ ላይ መጠነኛ ለውጥ አስተዋል ። የተከፋች ትመስላለች የምትለውን ለመስማት ቸኮለ

አንተ ሲፈልጉህ አትገኝም" አለችው "
“ ይኸው አለው” አለ እስንድር ፍርጥም ብሎ ።
" አትቁልድ እባክህ !
“ ቀለድኩ እንዴ ? ” አለ እስክንድር በልቡ አኳኋኗ ግራ ገብቶት አኳኋኗ ሁሉ ያኮረፈች ሚስት ዐይነት ሆነበት
በዝምታ ትንሽ ቆየች ፡ ስትንደረደር እንደ መጣችው ያሰበችን በአንዴ መዘርገፍ አልቻለችም ። እጀማመሩ ቸገራት
“ እስቲ ሻይ ጋብዘኝ ?
“ ፍራንክ አለኝ ብለሽ ነው ? ! እያለ ኪሱን ዳበሰ ።
ተአምር ይፈጥር ይመስል ፥ አታዋርደኝ ኪሴ ! ” አለ ። ግን ኪሱ ባዶ መሆኑን አላጣውም።

ከሌለህ፣ ግድ የለም ፤ እኔ ልጋብዝህ
አለችው ! ጭንቀቱ ታውቋት ።

"አዎ ይሻላል ” አላት ፡ መደናገጡን ለመሸሸግ እየሞከረ « የለኝም ማለት ለምን እንደሚያሳፍረው ወይም እንደሚያስደነግጠው ለራሱም ይገርመዋል።

ግቢ ውስጥ ወደ ሚገኘው ሻይ ቤት ሄደው ትንሸ ከቆዩ በኋላ ፡ ቤትልሔም ሻይዋን ፉት እያለች ፥ ጨዋታዋን ጀመረች

“ባገኘሁህ ቁጥር እነግርሃለሁ እያልኩ” አለችና አቋረጠች ።

"ምን አላት?"
"ጓደኛዬ እንድትሆን"
የሐፍረት ሣቅ ሣቀች “ ስሜቱን ለማጥናት ዐይኖቿን ፊተ ላይ ተከለች።

ከእስክንድር አፍ ጥያቄም ሆነ መልስ አልወጣም የሚያባብሉ ዐይኖቿን ማየት አፍሮ እንገቱን ሰበረ ። የተቆጣ እንዳይመስል ግድ ፈገግ አለ ። ምን ማለት እንደ ፈለገች በውል ሊገባው አልቻለም ።

“ አየህ እስክንድር እኔ እዚህ ግቢ ውስጥ ስሜ ጠፍቷል ። ኃጢያቴ አልገባኝም ። አንተ አስተዋይ ሰው ነህ በግቢው ውስጥም ጥሩ ስም አለህ ” አለችው በአንዴ ልውጥ ብላ ፥ ጭራሽ ድምጿ ወደ ለቅሶ እያደላ ።

“እና እስክንድር የተበላሸ ስም አዳሽ ነው እንዴ ? ? አለ በልቡ ። ግልጽነቷ ግን አስገረመው ። ምርጫ ሲኖረኝ ነው ራሳችንን የምንደብቅው ። ምርጫ ማጣት ሰውን ምን ያህል ግልጽ እንደሚያደርገው ትረዳ።

“አባባልሽ በደንብ አልገባኝም ”” ኣላት አፍ አፉን ስታየው የሚናገረው ጠፍቶት

መቼም እኔ እዚህ ግቢ ውስጥ በለማ እንደምታማ ታውቃለህ ” ?

“ አሃ ! አዎ ፡ ዐልፎ ዐልፎ አንዳንድ ወሬ እሰማለሁ።አላት ፡ አጠያየቋ የሚያውቀውን ለመካድ አስቸግሮት

እንዴት እንደምትቀጥል ተቸግረች ።

“ ለመሆኑ ፥ ከአስተማሪ ጋር መውጣት ወንጀል ነው እንዴ ? "ስትል እሱኑ ጠየቀችው

“ እንደዚያ ሳይሆን፥ ግንኙነቱ ከጥቅም ጋር ስለተያያዝ ነው ። እ! እንደምታውቂው ፡ እዚህ ግቢ ውስጥ የማርክ ነገር የተማሪዉ አንገብጋቢ ጥያቄ ነው ። እንኳንስ በሌላ ግንኙነት በጭንቅላትም መብለጥ አይወድም ። እና የጥላቻው
ምንጭ ይኸ ይመስለኛል ” ሲል ፊቷ ክፉኛ ተለዋወጠ።

“ እምልሽ ፥ እኔ ተማሪዉ ሲያወራ የሰማሁትን ነው ? አለ ፡ እንዳያስቀይማት ፈርቶ ።

“ ምቀኝነት ነው ! ” አለች ፥ ሳግ እየተናነቃት ።
“እኔ ማንም ተማሪ በዚህ መንገድ ይተረጉምብኛል ብዬ አላሰብኩም ነበር። ለማንኛውም አሁን ከለማ ጋር ግኑኝነታችን ተቋርጧል።.......

💥ይቀጥላል💥
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሰላሳ_አምስት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

...ትህትና ዛሬ ትንሽ ደሟ መለስ ብሎ ስትመለከት እናቷ ደስ አላት፡፡ ሰሞኑን ጥውልግልግ ብላ አስደንግጣት ነበር፡፡ ዛሬ ግን ሰውነቷን ተጣጥባ፣ ፊቷን ተቀባብታ፣ ምርጥ ለብሳ፣ ትህትናን መስላ ስታያት፤“ተመስገን” አለች በልቧ።
ያንን ምሽት እንደ አስታማሚ ልጅ ሳይሆን፤ እንደ ጥሩ አፍቃሪ ባል ፡ እቅፍ አድርጋት አደረች። ናፍቆቷን ሙሉውን ሌሊት አቅፋት በመተኛት ተወጣች፡፡
አሁን ሁሉንም ጣጣዋን ጨርሳለች፡፡ ዕቅዷን ልትፈጽም ሰዓቱ እየደረሰ ነው፡፡ በሌሊት ተነስታ ልብሷን ለባብሳ ጨረሰችና፣ ከፔርሙስ ትንሽ አጥሚት ቀድታ ካጠጣቻት በኋላ፤ “ወደ ቤት ልሂድ እማ!” ብላ ለመሄደ ተነሳች፡፡
ደግማ፤ ደጋግማ፤ ጉንጮቿን አገላብጣ ሳመቻትና፤ ወጣች፡፡ስትወጣ መንፈሷ ሁሉ ጠንካራ ነበር፡፡ ፍርሀት ጓዙን ጠቅልሎ ነው የሄደው፡፡ ቤት ደርሳ ያንን ትናንትና በፍቅር ስታሽሞነሙነው የዋለችውን የአባቷን ቅርስ ሸፋፍና፤ በቦርሳዋ ይዛ፤ ወደ መርካቶ ገሰገሰች፡፡
እዚያ እፍልሚያው ቦታ ስትደርስ ከታክሲ ወረደችና ራቅ ብላ ዓይኖቿን በሱቁ ላይ ተክላ ትጠባበቅ ጀመር፡፡
ልቧ ድው! ድው፤ ይላል፡፡ እልህና ሲቃ ይተናነቋታል፡፡ እንዷ ደቂቃ አቤት ርዝመቷ! አውሬው ወጥመዱ ውስጥ እስከሚገባ ድረስ በንቃት መጠባበቋን ቀጠለች፡፡
አንዳንድ ሱቆች መከፈት ጀምረዋል፡፡ እምብዛም ሰው አይታይም፡፡ መርካቶ ትንሽ ሞቅ ሲል እንደዚያ እንደማይተራመስ ሁሉ አሁን ያለው ሁኔታ የሚያስገርም ነው፡፡
ነጠላዋን ተሸፋፍና፣ መንገደኛ መስላ፧ አንድ ጥግ ላይ ተቀመጠችና፤ ግዳይዋን መጠባበቁን ተያያዘችው፡፡ በእርግጥም ስለቸኮለች ነው መሰል በጣም ቀድማ ነበር የመጣችው፡፡
ገንዘብ በገፍ እየገባለት የመጣው ጎረምሳ በንግዱ ላይ ትኩረቱን እየጣለ ሄዶ ነበር፡፡ አበራን ወደዚያ ካባረረ በኋላ ትርፉን ለግሉ ማግበስበስ ጀምሯል።
ገንዘብ ሲቀምሱት ይጣፍጣል፡፡ በላይ በላዩ ያስመኛል። እህል ሲጠግቡት ያስገሳል፡፡ሲበዛም ያስጠላል፡፡ ገንዘብ የሚጠግብ ሆድ ግን የለም፡፡ ግሳትም የለው፡፡ በላይ በላዩ ጨምሩልኝ፣ ጨምሩልኝ፣ የሚያሰኝ፣ እየበሉት የሚርብ ነገር ቢኖር ገንዘብ ነው፡፡
እንደሻው የራሱ የሆነውን፤ እንደፈለገው የሚያዝበትን ገንዘብ ሲያገኝ፤ እንደጠላት ገንዘብ ማውደም ሳይሆን፣ ቀስ በቀስ ሱቁን በማደራጀት ሀብታም መሆን ስለፈለገ፣ ቆጣቢና ትጉህ ሠራተኛ ሆኗል።
ዛሬ ከሌሎቹ ሁሉ ቀደም ብሎ ገበያ ሊሻማ መጣና የሱቁን በር ከፈተ፡፡ ሙሉ ጂንስ ለብሷል፡፡ ከላይ ጥቁር ክብ ባርኔጣ አድርጓል፡፡
አንገቱ ላይ አጠር ያለች ወፍራም ሻርፕ ጠምጥሞ ነበር፡፡
የሱቁን በር ከፍቶ ወደ ውስጥ መዝለቁን ስታይ ትህትና ተዘጋጀች፡፡ እሷም ጂንስ ሱሪ ነው የለበሰችው፡፡
ቀስ ብላ ቀኝ እጇን ወደ ቦርሳዋ ሰደደችና፣ ማጥበቂያውን አላላች፡፡ ሽጉጡ ላግዳጁ ዝግጁ ሆነ፡፡ አሁንም ቀስ ብላ ጨበጠቸው፡፡ እጇ የተንቀጠቀጠ መሰላት፡፡
“አይዞሽ ትህትና ጠንከር በይ” አለች ለራሷ፡፡ “የመጨረሻው ሰዓት የድል ሰዓት ደርሷል፡፡ የመጨረሻውን የድል ሰዓት ባትወጪው አበቃልሽ!” አለችና ራሷን አደፋፈረች፡፡
ይህ የመጨረሻው መክሸፍ የሌለበት እርምጃ ነው፡፡ በእውነትም ጠንከር አለች፡፡ ልቧ በትክክል መምታት ጀመረ፡፡ ሰውነቷ መራራ ደም ሲረጭ ተሰማት፡፡ የቀድሞ ባህሪዋ ከውስጧ ጥርግርግ ብሎ ወጣና፤ አዲስ የቆራጥነት፣ የደፋርነትና፤ የጭካኔ ባህሪይ ተላበሰች፡፡
“አምላኬ በደሌን አንተ ይቅር በለኝ፡፡ ነፍሴን ተቀበላት!” አለችና የሽጉጡን ምላጭ እንደያዘች እየተንደረደረች ወደ ሱቁ ሩጫዋን ቀጠለች፡፡
ሱቁ በር ላይ ስትደርስ እንደሻው በሚያየው ነገር ተደናግጦ፣ ዐይኖቹ ተበልጥጠው፣ አፉ ተከፍቶ እንደቀረ ትንፋሽ ከማውጣቱ በፊት
ሽጉጡን ላጥ አድርጋ አወጣችው፡፡
ንግግር የለ፣ ግርግር የለ፣ ፋታ ሳትሰጠው በቀጥታ እርምጃውን ወሰደች፡፡
ዷ! ዷ! ዷ! ዷ! አምስት የቆጠረች መሰላት፡፡ አራንቱን ጥይቶች ካንጣጣችበት በኋላ፣ ተንገዳግዶ መውደቁን ስታረጋግጥ፧ ሽጉጡን
ወደራሷ አዙራ አፍዋ ውስጥ አስገባቸው፡፡
ሰው መሯሯጥ ጀመረ፡፡ ለሚተራመሰው ሰው ቦታ ሳትሰጥ፤
እርምጃዋን በራሷ ላይ ወሰደች፡፡ ምላጩን ሳበቸው፡፡ ዷ! ዷ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሰማዩ የተባዘተ ጥጥ በመሰለው ደመና ተዥጐርጉሯል።
ጨረሯን የፈነጠቀችው ፀሐይ ያንን የደመና ቁልል እየናደችው ስትመጣ፤
ሰዓሊው በሸራ ላይ በብሩሹ የፈነጠቀው ንድፍ እየመሰለ ሄደ፡፡ ከዚያም ሙሉ ለሙሉ ደመናው ተገፈፈና፤ ጥርት ያለ ሰማይ ታየ፡፡
የሰው ልጅ የውስጥ ስሜቱ ሲጐዳ፣ ሲከፋው፣ ሲጨንቀው፤ ልክ ሰማዩ በደመና እንደሚያኮርፈው ሁሉ፤ ይህንን መጥፎ የውስጥ ስሜቱን በጨፈገገ ገጽታው ይገልጸዋል፡፡ በሆነ ባልሆነው ሆደ ባሻነት ያጠቃዋል፡፡
እነሆ ልቡ ከአምስት ዓመታት በላይ ከፍቅር ተገልሎ የቆየው ሻምበል ብሩክ ትህትናን ካገኘበት እለት ጀምሮ መንፈሱ ታድሶ!
የወደፊት የትዳር ህይወቱን በቅርብ ርቀት አሻግሮ መመልከት ሲጀምር፤ በእንጭጩ ተቀጨ፡፡
ትህትና ፍቅሯን ብቻ ሳይሆን፤ ያንን ደስተኛነቱን ጭምር በልቡ ውስጥ ገድላበት ነው የሄደችው፡፡
ድምጿን ለመስማት ይፈልጋል፣ ወዲያውኑ ደግሞ ከነመፈጠሯ እንዲረሳት ይመኛል፡፡ ትናፍቀዋለች፤ የሠራችው በደል ፊቱ ላይ ድቅን
ይልበታል፡፡ በቅናት ይቃጠላል፡፡ ወዲያውኑ ደግሞ ብሩኬ.... ብሩኬ....
ብሩኬ.... የሚለው ያ ለስላሳ ድምጿ፣ ያ ለስላሳ ሰውነቷ ያ ለስላሳ ባህሪዋ፤ ይታወሰዋል፡፡
በፊት የነበረችው ትህትና እንዴት የምትወደድ ልጅ ነበረች? ለምን ፈጣሪ አሳይቶ ነሳው? ምነው እሱ ለፍቅር አልታደለ? ሁል ጊዜ መጨነቅ?
“ምነው የዚያን ዕለት ባልተገናኘን ኖሮ” የሚል ሃሣብ መጣበት፡፡ ሆኖም በመገናኘታቸው አንድ መልካም ሥራ መስራቱ ያስደስተዋል፡፡
አጋር ያልነበራት እናቷን መርዳት መቻሉ እርካታን ይሰጠዋል።
ጽድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም
ከክፋት ደግነት ሳይሻል አይቀርም፡፡ እንዲሉ፣ እሷ ትበድለው እንጂ፤ እሱ ከበደል ይልቅ መልካም ሥራን የሠራ ተበዳይ መሆኑ ሲታወሰው፤ “ይሁን እስቲ ሁሉ ነገር ከፈጣሪ ይገኛል” ይልና
ይጽናናል፡፡
እንደ እውነቱ ከሆነ የሰሞኑ ሁኔታው የተለየ ነበር፡፡ ናፍቆቷ ነፍሱን ሊያወጣው ደርሷል፡፡
በውስጡ ፍቅርና ጥላቻ ነግሰውበታል፡፡ እንዳይጠላት ይወዳታል፣ እንዳይወዳት ደግሞ የሠራችው ሥራ...እንዳንድ ጊዜ ያ አለቃቀሷ፤ እዚያ እላዩ ላይ ተጠምጥማ እየተንሰቀሰቀች የተናገረችው ንግግር፣ ትዝ ይለውና፤ “ምን ነበረበት ይቅር ብላት ኖሮ? ግብዝ ነኝ” በማለት እራሱን
ይኮንናል፡፡ ወዲያው ደግሞ የሻክረና ጥርጣሬ የገባው ልብ ተመልሶ ልብ
ላይሆን፡፡ የነቃ ብርሌ ተመልሶ ዕቃ ላይሆን፣ አጉል ሙጥኝ አለማለቱን
ይወደውና..
እንኳንም በጊዜ አቋረጥን” የሚል ስሜት ይሰማዋል፡፡በጠዋቱ መ/ቤቱ እንደደረሰ ወደ ቢሮ ከመግባቱ በፊት ጫማውን
ሊያስጠርግ ሄደ፡፡ሰማዩን አየው፡፡ ከቤት ሲወጣ በደመና የተሸፈነ ነበር፡፡ አሁን
ግን ጥርት ብሏል፡፡ የሱ ስሜት ግን እንደሰማዩ አልጠራም፡፡ ፊቱ ጨፍግጓል፡፡ ጫማውን አስጠርጐ ወደ መሥሪያ ቤቱ ግቢ ሲዘልቅ......
“እንደምን አደርክ ሻምበል መልዕክት አለህ” አዳሪው ፖሊስ ከኪሱ ውስጥ ያስቀመጠውን ፖስታ አቀበለው፡፡
ሻምበል ፖስታውን ተቀብሎ ተመለከተው፡፡ የላኪው ሥም
የለበትም፡፡
የአደራ ደብዳቤነቱን እንጂ ከማን እንደተላከ አይገልጽም፡፡
“ማን ነው የሰጠህ?” ሲል ፖሊሱን ጠየቀው፡፡ ስሟን እንዳልነገረችው ገለፀለት፡፡ በቀጥታ ወደ ቢሮው ሄደ፡፡
የቢሮውን መስኮት ከፈተው፡፡ ንፁህ አየር ገባ፡፡ ከዚያም
👍1
መለዮውን አውልቆ፤ ጠረጴዛው ላይ ካኖረው በኋላ፤
የዚህን እንግዳ የሆነ ደብዳቤ ይዘት ለማወቅ ጓጉቶ፤ ፓስታውን ቀደደው፡፡
“እንደምን አደርክ ሻምበል ገብተሃል እንዴ?” የጣቢያው አዛዥ ወደ ቢሮአችው ሲሄዱ እግረ መንገዳቸውን ሰላምታ ሰጥተውት አለፉ፡፡
እግዚአብሔር ይመስግን ሻለቃ ደህና አደሩ?” አፀፋውን ቆሞ ሰላምታ ከሰጠ በኋላ ወደ ደብዳቤው ተመለሰ፡፡
ሻምበል ብሩክ ደብዳቤውን ማንበብ ሲጀምር ሰውነቱ እየተለዋወጠ ሄደ፡፡ ቀስ በቀስ ልቡ ታርዶ እንደተጣለ ዶሮ ትንደፋደፍ ጀመር፡፡ በመደናገርና በድንጋጤ ስሜት እንደተዋጠ ንባቡን ቀጠለ፡፡ ወደ ዝርዝሩ በገባ ቁጥር ደርዘን ፍርሃትና ጥርጣሬ እየተጫነው ሄደ።
ይህ ጭንቀቱ በግንባሩ ላይ ላብ ችፍ፤ ችፍ፤ ያስደርገው ጀመር፡፡ ከዚያም የሆነ ቦታ ላይ ሲደርስ ወረቀቱን አጥፎ ዐይኖቹን ጨፈነና..
“እፎ ይ ይ ይ ......” ሲል በረጅሙ ተነፈሰ፡፡ ልቡ ትር ትር ትር አለች፡፡ “ወይኔ ብሩክ ምን ተአምር ነው የማየው? ወይኔ የበላይ ልጅ፤ ነፍሰ ገዳይ ልሆን ነው ማለት ነው?
እውነት ትህትና ጨክና እራሷን በራሷ ልታጠፋ ነው ማለት ነው?”
እናቷ ሆስፒታል ውስጥ እያለቀሰች ታየችው፡፡ ወንድሟ አንዱአለም ፊቱ ላይ ድቅን አለበት፡፡
“አንተ ነፍስ ገዳይ እህቴን ገደልካት” ብሎ ጣቱን ሲቀስርበት ታየው። ዝቅ እያለ ሄደ። ኸረ በፈጣሪ? አገር ጥላ ኮበለለች? ትህትና እራሷን አታጠፋም! ባይሆን ወደ አንድ የማይታወቅ ቦታ ሄዳለች ማለት
እንደሻው? እንደሻው? የዚያን ጊዜ አንገቱ ላይ ተጠምጥማ እያለቀሰች የነገረችው ትዝ አለው፡፡ ልክ ነበር ማለት ነው? ትህትና አልዋሸችኝም ነበር ማለት ነው?
ወይኔ ብሩክ ጥይት ተኩሼ ባልገድላትም ገዳይዋ እኔው ነኝ፡፡ ወረደ ልክ ነው፡፡ ወደ መጨረሻው ሲቃረብ በጭንቅላቱ ወስጥ የሆነ ነገር የፈነዳ መሰለው፡፡ አይኖቹን
ጨፈነና ትንሽ ቆይቶ ገለጣቸው፡ አልቀረለትም :: የጠረጠረው ሆኖ አገኘው፡፡

ስሜቱ ተናወጠ፡፡ አእምሮው በጭንቀት ሊፈርስ ተቃረበ፡፡ ዐይኖቹን አሁንም ጨፈነ፡፡ እንደገና ገለጣቸው፡፡ እንደገና ጨፈናቸው...
እንደገና በመጨረሻው ብዥ ብዥ ብዥ... የሚል ነገር ታየው፡፡ አስፈሪው የስንብት ቃል! ሲያነበው እያንዳንዱ ፊደል ጦር ሆኖ አእምሮውን አየሰቀሳቀ፤ እየወጋ፤ አቆሰለው፡፡ የዚያች የንፁህ ልጅ
የስንብት ቃል......
“እወድሃለሁ ብሩኬ፡፡ የመጀመሪያም የመጨረሻም ፍቅሬ አንተ ነበርክ፡፡ ደህና ሁንልኝ....”
“ሁሉ ነገር አልቋል መርካቶ
“ወይኔ ብሩክ!” እንደ እብድ ወንበሩን ወደዚያ አሸቀንጥሮ ወደ አለቃው ቢሮ ሮጠ፡፡
“እባክዎትን ሻለቃ አንድ ጊዜ የመኪና ቁልፍ ይስጡኝ?” ሰውነቱ
ይንቀጠቀጥ ነበር፡፡
ሻለቃ ሁኔታውን ሲያዩ ደነገጡ፡፡ያልተለመደ ሆኔታ ይታይበት
ነበር፡፡ “ምን ሆነሃል ሻምበል? አይዞህ ረጋ በል” ከወንበራቸው ተነስተው፡፡ ድምፁም ልክ እንደሰውነቱ ይንቀጠቀጥ ነበር።
የሱን ሀኔታ ሲያዩ ሻለቃ ሃሣባቸውን አስተካከሉ፡፡ በዚህ ሁኔታ መኪና ይዞ ቢሄድ አደጋ እንዳይደርስበት ስለፈሩ የአሥር አለቃ ዓለማየሁን ጠርተው ......
“እንካ ቁልፍ፡፡ ሻምበልን የሚፈልገው ቦታ አድርሰው፡፡ ረጋ ብላችሁ ሂዱ ታዲያ! " ሲሉ ትዕዛዝ ሰጡት፡፡ ከዚያም ወደ መርካቶ ይከንፉ ጀመር፡፡

ሻምበል ብሩክ ሩጫው ከንቱ ... ጥረቱ ዜሮ የምትወደው ጓደኛው ትህትና... ጀንበሯ ጠለቀች? ወይስ?
እየበረሩ መርካቶ ገበያ አዳራሽ አጠገብ በህዝብ የተጨናነቀ ስፍራ ደረሱ::
“ቱፍ! ቱፍ! በሞትኩት እኔን! እኔን!
ወይኔ ምን ብታደርገው ነው? ያቺን አበባ የመሰለች ልጅ?.....”
“አቤት! አቤት! እንዴት ያለው አሳዛኝ ታሪክ ነው? አሁን ይሄ የሰይጣን እንጂ ፤ የሰው ሥራ ይሉታል? የጋኔን ስራ እንጂ! ያንተ ያለህ ድብን አድርጓት ለራሱም ጠጣው አቤት! አቤት!”

ግማሹ ከንፈሩን ይመጣል፣ ገሚሱ ደረቱን ይደልቃል፡፡ ወደ ስማይ ወደ ፈጣሪ እያንጋጠጠ....
“ወንድ ነው! እኔ በበኩሌ አደንቀዋለሁ!! አንጀቱን አሳርራው ይሆናል ዋጋዋን የሰጣት! በቁሙ ተቃጥሎ ከሚሞት፤
አቃጥሏት መገላገሉ በጀው”፡፡ የጉርምስና ስሜት ከሚታይባቸው መካከል
የሚሰነዘር.... እንደዚያ ሰው ተሰብስቦ የሚንጫጫበትን እየሰነጠቀች አንዲት የፓሊስ ሠሌዳ ቁጥር ያላት ቮልስ ዋገን መሀል ገብታ ቆመች፡፡ ሻምበል ብሩክ ፊቱ ጥላሸት መስሎ፣ ዐይኖቹ በድንጋጤ
እንደተጐለጐሉ፤ ከመኪናው ላይ ዱብ ብሎ ወረደ፡፡ አብዛኞቹ በፍርሃት
ገለል ገለል አሉ፡፡ የሚታፈሱ ነው የመሰላቸው፡፡

“ምን የተፈጠረ ነገር አለ? ምንድ ነው!” አንዱን ጐረምሣ ቢጤ አፋጠጠው፡፡
ለሱ አልታወቀውም እንጂ ልጁን እንደ ነፍሰ ገዳይ ኮሌታውን ጨምድዶ ይዞት ነበር፡፡
“ተጋደሉ በጥይት ወንፊት አደረጋት” አንገቱን ለማስለቀቅ እየሞከረ፡፡
“ማን ነው ማንን ወንፊት ያደረገው?” ተገላቢጦሹ ግራ ገባው።
“አትቀባጥር! ቀባጣሪ! ለወሬ ከመሽቀዳደምህ በፊት አጣራ!
ወሬኛ!” አለና አንዱ ጎረምሣ ልጁን ወደዚያ ገፍትሮ ወደ ሻምበል ብሩክ
ጠጋ አለ፡፡
“ጌታዬ እሷ ናት የመታችው፡፡ ደጋግማ ከተኮሰችበት በኋላ ለራሷ ጠጣች፡፡ በጣም የሚያሳዝን ነገር ነው፡፡ ይህን በዐይኔ በብረቱ ነው ያየሁት” አለና ምስክርነቱን ሰጠ፡፡
“ሞታለች?” ሻምበል ስውነቱ በብርክ እየተንቀጠቀጠ፡፡ ትሙት ትኑር አላውቅም፡፡ ከዚህ ወደ ሆስፒታል ሲወሰዱ ግን ሁለቱም በህይወት ነበሩ፡፡ የሚተርፉ ግን አይመስለኝም፡፡”

“የት ሆስፒታል ነው የተወሰዱት? ና እስቲ ግባ” ልጁን መኪና ውስጥ አስገባው፡፡ሁለቱም ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል መወሰዳቸው ተነገረውና፤ ተያይዘው ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በረሩ፡፡ሻምበል ብሩክ ነፍሱን አያውቅም፡፡ ሆስፒታል ደርሰው ወዲያና ወዲህ እየተራወጡ ስለ ሁኔታው ጠየቁ፡፡

አንዲት ነጭ ካፖርት የለበሰች ነርስ የሆነውን ቀስ ብላ አስረዳችው፡፡ ሁለቱም ጉዳተኞች በህይወት እንደሚገኙና በድንገተኛ ህክምና ክፍል እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ረጋ ብላ ገለፀችለት፡፡
“እውነትሽን ነው? አልሞተችም?” በሁለት እጆቹ ትከሻዋን ይዞ በጉጉት ጠየቃት፡፡
ይመኑኝ በተለይ እሷ ለህይወቷ የሚያሰጋ ጉዳት እንዳልደረሰባት ሀኪሞቹ ሲናገሩ በጆሮዬ ሰምቻለሁ፡፡” . ነፍሱን ትንሽ
መለስ አደረገችለት፡፡

“ምን እናድርግ አሁን ሲስተር? ደም የሚጠየቅ ከሆነ እባክሽን አጣሪልኝና
ደም ልስጥ፡፡ ሌላም የሚያስፈልገውን እርዳታ ሁሉ አሳውቂኝ፡፡ ሲስተር ትልቅ ባለውለታዬ ትሆኛለሽ፡፡ ተባበሪኝ” ተማፀናት፡፡

“ግድ የለዎትም አይረበሹ፡፡ የሚሆነውን ሁሉ በዶክተሮች ትዕዛዝ መሠረት እንፈጽማለን፡፡ እስከዚያው ይምጡ” አለችና ወስዳ አንድ ክፍል ውስጥ አረፍ እንዲል አደረገችው፡፡
ሁኔታው ስላሳዘናት ነው ትንሽ እረፍት እንዲወስድና፤ እራሱን እንዲያረጋጋ፤ የፈለገችው፡፡
ሻምበል ብሩክ አምላክ ነፍስ ገዳይ እንዳያደርገው በልቡ ፀሎት እያደረሰ፣ የሚሆነውን ሁሉ በሲስተር ማን አህሎች በኩል ለመሰማት በጉጉት መጠባበቁን ቀጠለ፡፡
“መኪናውን ይዘህ ሂድ” አለና ሾፌሩን ሸኘው፡፡ ለልጁ አምስት ብር አስጨብጦ ሁለቱንም ላክና፤ እሱ እዚያ ሆኖ ውጤቱን ይጠባበቅ ጀመር፡፡ አሁን ትንሽ ነፍሱ መለስ ስትልለት፤ አንድ ነገር ትዝ አለው፡፡
ለአዜብ እንዲደውልላት አደራ ብላው ነበር፡፡ የስልክ ቁጥሩን ከደብዳቤው ላይ አነበበና ለአዜብ ደወለላት፡፡ ዝም ብሎ በደፈናው ችግር መድረሱን ገልጾ፤
ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በአስቸኳይ እንድትመጣ ነገራት፡፡
አዜብ ይህንን ስትሰማ ክው ብላ ደንገጠች፡፡ አንዱአለም የሞተ መሰላት፡፡ ነፍሷን ሳታውቀው፤ ፀጉሯን እንኳን ሳታበጥር፤ እየከነፈች መጣች፡፡ ሻምበል ብሩክ በሩ ላይ ሆኖ
👍2
እየጠበቃት ነበር፡፡
“አንዱዓለም ሞተ?! ሞተ ሻምበል?!” ሰውነቷ ተረብሿል። እዚያ እሱቁ ድረስ ወስዳ እንደሻውን ያሳየችው እሷ ነች፡፡ ጦሱ የሷ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ሲሞት እሷ እንደገደለችው እየተርበተበተች ፤ ሻምበልን አፋጠጠችው፡፡

የተፈጠረው ተአምር ግን ከግምቷ ውጭ
ነበር፡፡ጭራሽ ይሆናል ብላ ልትገምተው የማትችለው አስደንጋጭ ሁኔታ! ሻምበል
እንዴት እንደሚገልጽላት ጨንቆት ዐይኖቹ ፈጠው ቀሩ...
“አንዱዓለም ምንም አልሆነም፡፡ አዜብ ሌላ ነገር ነው ትህትና እንደሻውን በጥይት ከመታችው በኋላ፣ እራሷን
“እናስ ከዛስ? እራሷን ምን?!!!...ጮኸች፡፡
“አራሷንም በጥይት ጐድታለች..

ኡይይ! ሞታለች በለኝ እንጂ ሻምበል! ጓደኛዬ ሞታለች በለኝ እንጂ!ትሁትዬ፣ ያልታደለችው ጓደኛዬ ሞታለች፡፡ ትሁት ሞታለች፣እንደሰው ሳይደላት እንደተቃጠለች ሞተች፡፡ እንዳለቀሰች ቀረች ጓደኛዬ ትሁትዬ? የት ነው ያለሽው? የኔ እመቤት! ጓዱ .... ጓደኛዬ እንደ እብደ ሆና እየጮኽች ወደ ግቢው ውስጥ ሩጫ ጀመረች፡፡
ሻምበል ተከትሏት ሮጠና፤ በግድ አጇን ይዞ አስቀራት፡፡ ወዴት ልትሄድ እንደነበረ እግዜር ይወቀው፡፡ እዚያ እመሬት ላይ ወድቃ በእንባ እየታጠበች አለቀሰች፡፡ የማትለው፤ የማትናገረው፤ ነገር የለም፡፡ ትህትና በህይወቷ አንድም ቀን ሳይደላት፤ እንደተሰቃየች፣እንደተቸገረች፣እንደተንከራተተች፤ መሞቷን፣ የሷ ደስታ ከሻምበል ጋር ያሳለፈችው አጭር ወቅት ብቻ መሆኑን፣ እየለፈለፈች አለቀሰች፡፡
ሻምበል አልቻለም፡፡አንጀቱ ከውስጥ ተንሰፈሰፈ፡፡ ድምፁን ውጦ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ፡፡ በአንድ በኩል እሱ እራሱ አልቃሽ፤ በአንድ በኩል ገላጋይ ሆነ፡፡
“እባክሽ ዝም በይ አዜብ፡፡ ደህና መሆኗን አረጋግጫለሁ፡፡
ለህይወቷ እንደማያሰጋት ተነግሮኛል። እባክሽ ዝም በይ” እንደዚያ ሆና በምሬት ስታለቅስ፤ በትህትና ላይ የደረሰው
የህይወት ፈተና፣ ስቃይዋ፣ እራሷን እስከማጥፋት የሚያደርስ መከራ
መሸክሟ፣ ንፁህነቷ፤ በሃሣብ ታየው፡፡
በተለይ እላዩ ላይ ጥምጥም ብላ፤ ስቅስቅ ብላ! ያለቀሰችው፣ እፊቱ ላይ ድቀን ቢልበት ... ሰውነቱ ተንቀጠቀጠ፡፡
አዜብ ትንሽ ቀዝቀዝ ስትል፤ ስለሁኔታው ከሀኪሞች አንደበት እንድትስማ! ወደ ሲስተር ማን አህሎሽ ዘንድ ይዟት ሄደ።
ሁሉንም አዜብ ትነግርሃለች ብላው ነበር፡፡ስለሁሉም ሁኔታ ዝርዝሩን ከአዜብ ሊሰማ፤ ደብዳቤውን ሰጣት፡፡ አዜብ ያንን ደብዳቤ እያለቀሰች አንብባ ከጨረሰች በኋላ፤ የሆነውን ሁሉ፤ አንድም ሳታስቀር እውነታውን ተረከችለት....

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
አትሮኖስ pinned «#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ ፡ ፡ #ክፍል_ሰላሳ_አምስት ፡ ፡ #ድርሰት_በትክክል_ገና ...ትህትና ዛሬ ትንሽ ደሟ መለስ ብሎ ስትመለከት እናቷ ደስ አላት፡፡ ሰሞኑን ጥውልግልግ ብላ አስደንግጣት ነበር፡፡ ዛሬ ግን ሰውነቷን ተጣጥባ፣ ፊቷን ተቀባብታ፣ ምርጥ ለብሳ፣ ትህትናን መስላ ስታያት፤“ተመስገን” አለች በልቧ። ያንን ምሽት እንደ አስታማሚ ልጅ ሳይሆን፤ እንደ ጥሩ አፍቃሪ ባል ፡ እቅፍ አድርጋት አደረች።…»
#ሰመመን


#ክፍል_ሃምሳ


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

....ለማንኛውም አሁን ከለማ ጋር ግንኙነታችን ተቋርጧል።

"በቃ?"

" አዎ " ከእንግዲህ በዚህ አይነት የምንቀጥል አይመስለኝም ። በእሱ የተነሣ ነው ፡ እንዲህ ስሜ የጠፋው ። ”

ሁለቱም ዝም አሉ። እስክንድር ለሁኔታው ያልተዘጋጀበት ሆኖ ነው ለአፋጣኝ ጥያቄም ሆና መልስ የተቸገረው።
ቤተልሄም ግን በዝምታው መርከብ ተሳፍራ ወደ ኋላዋ ከለማ ጋር የተጣሉበት ቀን ደርሳ ነበር።

የሁለተኛ ሴሚስተር ትምህርት ተጀምሮ ልማ ምንም ኮርስ እንደማያስተምራት ካረጋግጠች በኋላ ፥ ቤተልሔም ሸርተት ለማለት ትጀምራለች ። ጭራሹን ለአንድ ሳምንት ያህል ትሰወርበታለች።ለማ ልቡ ይጠረጥርና በዚያው ሳምንት ግቢ ውስጥ ፈልጎ ካገኛት በኋላ ፥ ቤቱ ድረስ እንድትመጣ ነብር ሆኖ ይቀጥራታል ።

"ምን ሆነሽ ነው እንዲህ የጠፋሽው!" እንደ ብራቅ ጮህባት።
"ስላልተመቸኝ ነው"
"ይህው ነው መልስሽ?" አላት በሽቆ።
ዐይኗን ሰብራ ዝም አለች ። አኳኋኑ አስፈራት ። ገላጋይ በሌለበት ባዶ ቤት ውስጥ የያዛት እንደሆን ማን ይደርስላታል ? ሽንቷ ወጠራት ።
"ምን መሰለህ ለማ" አለችው እንባ በተናነቀው ድምፅ ዬኒቨርስቲዉ ውስጥ ስሜን እያጠፉ ነው ። ከአንተ ጋር ባለኝ ግንኙነት ክፉኛ ታምቻለሁ ። ሰላም ይሉኝ የነበሩ ተማሪዎች ሁሉ ዘግተውኛል !
"እና ? ”
“ እና ለአንተም ስም ሆነ ለእኔ ይህን ግንኙነታችንን ብናቋርጠው ይሻላል ብዬ ነው። እኔ እዚያ ግቢ ውስጥ መኖር
እልቻልኩም ፡ ሰውነቴ አለቀ” አለችው ፡ ለቅሶ እየቃጣት
እንዲሁ ነች ። እስክንድርን ጠርታ ፥ “ ጓደኛዬ ሁን ” እንዳለችው መሆኑ ነው ። ብልጠቷ ስልት የለውም ። ይህ ስልት ያጣው ብልጠቷ ለማን አብከነከነው ።

“ ስሚ ! ” አላት ። መቀጠል አልቻለም ። ጉሮሮው ላይ የሆነ ነገር ተናነቀው ። ከወጣትነት ባለፈ ዕድሜው የእልህ ዕንባ እንዳያነባ ፈራ ። እናም ከምላሱ ይልቅ እጁን ማንቀሳቀስ መረጠ ። የራስጌ ኮመዲኖውን ከፍቶ አንድ ወረቀት አወጣና ሰጣት ።

ምንድነው ? አለችው ።
አንብቢው ! አላት ፡ ዐይኑን አፍጥጦ ።

በዚሁ ሳምንት ውስጥ ቢሮው ወስጥ በድብቅ ተጥሎ ያገኘው ወረቀት ነበር ። ቤተልሔም ተቀብው ማንበብ ጀመረች።

ጽሑፉ በቅጡ አልተቀነባበረም ። በግጥም ይጀምርና
ምሁር ሰማ ዘቀጠ ...

ኅሊናውን ለሴት ሽጠ ...

ካለ በኋላ ፥ በስድ ንባብ ይቀጥላል ። ቃላቱ ተስፋ መቁረጥን ያመለክታሉ ። በለማ ላይ የተደረደሩ ተራ ስድቦች ነበሩ ።
በመሐል ደግሞ

... ወሲብ አንጎል ሆኖ ሲያስመርቅ እያየሁ ፡ የእኔ ጥናት ከንቱ እንዲያው ተሠቃየሁ አወይ እኔ ፡ አወይ እኔ ! ሴት አለ መሆኔ !...” ይልና፡ ተመልሶ ስድቡን ይቀጥላል ።

አንብባ ጨርሳ ቀና ስትል፥ የምትናገረውን ለመስማት ዐይን ዐይኗን ተመለከታት ። ለእሷ ሲል የተጋፈጣቸው ችግሮች በውስጧ ኅዘን እንዲፈጥሩባት ነበር ሃሳቡ ። እንዲህ ዐይነት ነገሮችን ሥራዬ ብሎ ነው የሚነግራት ። አንዴም በመጀመሪያው ሴሚስተር አንድ ጓደኛው መቼም የቅርቤ ነው ብሎ ሊመክረው ፥ “ ለማ እዚህ ግቢ ውስጥ በአንዲት
ልጅ ምክንያት ስምህ እየተበከለ ነው ” ብሎ ሲጀምር' ለማ በሽቆ ፡ “ ስለዚህ ጉዳይ ምንም አታንሣብኝ ። ተፈጥሮን
ተመክሮ አይመልሰውም ! ማንም የፈለገውን ሊል ይችላል” ብሎ ዘግቶታል ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ መምህራንም
እየታዘቡት መሆናቸውን ሊነግረው ነበር ጓደኛዉ የፈለገው ነገር ግን ለማ የሚበገር ሰው አልሆነም።

በወቅቱ ይህንንም ለቤተልሔም አጯውቷታል ።በአንቺ የተነሳ ያየሁት አበሳ" አይነት መሆኑ ነው። ታዲያ ያኔ ቤተልሄም አዝና ከንፈሯን መጥጣለት
ነበር ።

"አበሻ ነገር መፈትፈት ልማዱ ነው ! አትጨነቅ ” በማለትም አበረታታዋለች ። አሁን ግን ግጥሙን አንብባ የዚያን ዐይነት መልስ አልሰጠችውም ፡፡ እንዲያውም ለአፍራሽ ሐሳቧ መንገድ የጠረገላት ነው የመሰላት......

እና ፥ ከዚህ ሁሉ ነገር በኋላ ወዴት ነው። ሸርተት የምትይው ? አላት አፍጥጦ።

“ እኔስ የፈራሁት ይህንኑ አይደል ? ” አለችና ጽሑፉ ክፉኛ እንደ ቆረቆራት ሁሉ ዐይኗን አሸች ። ዕንባው ደግሞ ራሱ ካልፈቀደ እንደ ፈለጉት አይመጣ ! ዐይኗን ምራቅ እንዳትቀባ ለማ አጠገቧ ቆሟል።

መጀመሪያ ለምን ነበር የቀረብሽው ? ” አላት እስክንድር።

" ፈራሁኛ ! ”
"ምን ? "
"ማትስ እንዳልወድቅ ። እኔ የቁጥር ዘር ጠላቴ ነው ።

ፍቅር ብቻ ሳይሆን እልህ ጭምር ነበር የያዘው ። አስተያየቱ አላማራትም ጡንቻው ላይ አባብጠው የተጋደሙት
ሥሮች አሰፈሯት ። ከተቀመጠችበት ቀስ ብላ ተነችና ወደ በሩ አምራች ።

የት ልትሔጂ ነው ? ” አለና ፥ አጠገቡ የነበረውን አምቦ ውሃ ጠርሙስ አንስቶ ግንባሯ ላይ አነጣጠረ።
“ውይ ለማ ! ” ብላ ጮሃ ጣውላው ላይ ቁጭ አለች ።
“ ሸርሙጣ ! ” አላት አጠገቧ ደርሶ ቁልቁል እየተመለከታት
የሚለማመጡና የተቆጡ ዐይኖች ሽቅብና ቁልቁል ተፋጠጡ ። ለማ ደፍሮ እጁን ሊያሳርፍባት አልቻለም ። አቅፎ
ለማባበልም ልቡ ያን ያህል አላላም ።

"ስሚ ፤ በሦስት ቀን ውስጥ አስበሽበት መልሱን ንገሪኝ። የሦስት ቀን ዕድሜ ሰጥቼሻለሁ ! ” አላት እንዳፈጠጠ ።

ቤተልሄም ከጣውላው ላይ ቶሎ አልተነሳችም” በድንጋጤ ከጭኗ ሥር ሽንት ጠብ ያለ ስለ መስላት እንዳይታይባት ፈራች ። ነገር ግን ሰውነቷን ዐልፎ ጣውላው ላይ
የደረሰ አልነበረም...

ያን ዕለት እንደ ምንም ከክፍሉ ከወጣች በኋላ መንገድ ላይ በጕዳዩ እሰበችበት ። የይህሆን ጨዋታ ነው ። የለማ ኮንትራት አልቋል ። አብራው ከቀጠለች ለሚቀጥሉት ዓላማዎቿ ዕንቅፋት ይሆንባታል ። ከአንድ ወንድ ጋር ብዙ መታየት ሴሎች የጥቅም መንገድን ወመዝጋት ነው ። ጥቅሙን የሚያሳድድ ሰው በአንድ ነገር ላይ መርጋት አይችልም ትርፉን ከኪሳራው እያሰላ በሚያዋጣው መንገድ መንቀሳቀስ አለበት ... እና ለማ እስኪረሳት ድረስ ከዐይኑ ለመሰወር ወሰነች። ከዚህ ውሳኔ በኋላ ስሟን ለማደስ በግቢው ውስጥ አብራው
የምትታይ ተማሪ ስታስብ ፥ እስክንድር በሐሳብዋ ብቅ አለ ። ብዙ ተማሪዎች ከዘጓት በኋላ እሱ ሳይለወጥ እንደ
ወትሮ ሰላም ይላት ስለ ነበር ነው የታሰባት......

እስክንድር በሆዱ ሣቀ። የግልጽ ሰው ሳይሆን የብልጥ አንበሳ ምስል ከፊቱ የቆመ መሰለው ለጥቅም የቆመች
አንበሳ ! ሣር ባየችበት ሁሉ የምታጎነብስ በግ ፤ ግን ደግሞ እንስሳ ለማዳ ነው ያበላውን ያጠጣውን ፥ የቀረበውን ቶሎ
ያፈቅራል ።

«ግን ታዲያ አብራችሁ ስትቆዩ ከለማ ጋር ፍቅር አልያዘሽም ? ” ሲል ጠየቃት ።

“ ኤጭ ! ” አለች በንቀት
"እሺ ፤ እሱስ ፍቅር ቢይዘው ኖሮ ? ”

“ እእይ እኔ አስቀድሜ ነግሬዋለሁ" አለች ግንባሯን አኮማትራ
"ምን ብለሽ ?
“ አሜሪካ የመሔድ ሐሳብ እንዳለኝ እጮኛዬ እየጠበቀኝ ነው።
ሣቁ እንዳያመልጠው እየሞከረ ፥ ዋና ይዘሽ በትርፍ እየተጫወትሽ ነዋ ! ” አላት
ፈገግ ብላ ዝም አለች ።

“የእኔም ጓደኝነትስ ምሽን እስካሳደርስሽ ድረስ ነዋ!”አላት ድንገት ግልፍ ብሎት ።

ወይኔ ! ካንተ ጋር እኮ እንዲሁ ጓደኝነት ነው ” አለችው ፥ ድንገተኛ ቁጣው አስደንግጧት ።

“ እንዲሁ ጓደኝነት ብሎ ነገር ምንድነው?” ሲል አሰበ። ሐሳቡ ከውስጥ ጥቀርሻ እየለበሰ ሲመጣ ተሰማው ። የአሁኗ
ቤተልሔም ሳትሆን ነገ የምትይዘው ቦታና የምትፈጽመው ተግባር ነው የታየው በዚህ ዐይነት ብላሽ ጥበብ ከዩኒቨርስቲ የምትረቅ ሴት ፥ በሥራ ዓለም ስትሠማራም መሰሎቿን ታፈራና ትመለምል እንደሆን እንጂ ያስተማራትን ሕዝብ
👍4
ምን ያህል ትረዳለች ? ”

አንቺና መሰሎችሽ ተመርቃችሁ በምትይዙት ቦታም የኅብረተሰቡ በሽታ ነው የምትሆኑት ! ሊላት ፈለገ ። ግን
በምላሱ እንዲህ አምርሮ ሊያስቀይማት አልደፈረም ። “ ይልቅስ ለምን ቀርቤያት ከጥፋቷ እንድትማር አላደርጋትም ?
ሴት ልጅ ውበቷንና ገላዋን ለፍቅር እንጂ ለጥቅም መሸጥ የለባትም ፡ ካለዚያ ውሎ ሲያድር እንደ ዕቃ መቆጠር ይመጣል ብዬ ለምን አልመክራትም ? እንዲህ ዐይነቱ ከንቱ ብልጠት ከቤተልሔም ጋር አብሯት አልተወለደ ፤ ከኖረችበት አካባቢ የቀሠመችው በሽታ ነው እንጂ " እኔ ከማግለል ማስተማሩ አይሻልም ? ” የሚል የኅሊና ሙግት ገጠመው ።

ከሐሳቡ በስተጀርባ የችኮላ ስሜት ወጥሮት ነበር ።ወዴት ለመሔድ እንደ ቸኮለ አልገባውም። የሚሔድበትም
ጉዳይ አልነበረውም ።ከትዕግሥት ጋር የተያያዘ ስሜት ነበር የወጠረው ። እሷ ለአል ደብዳቤ ልትጽፍለት መሆኑን
ለቅርቡ ሰው አጫውቶ ተንፍሶ እንዲወጣለት ይፈልጋል ግን ለማን ? ለአሥራት ? ለቢልልኝ? ለዮናታን ?...

"ምነው ዝም አልክ ? ” አለችው ቤተልሄም ዝምታው አስከፍቶአት።

"እእይ ፤ እንዲሁ ነው" አለና "ግድየለሽም
ግኝኙነታችን እንደ ጥንቱ ቢቀጥል ይሻላል ” አላት እያመነታ።

አኩርፋ ለመሄድ ተነሣች።
“ እፎይ ትሒድልኝ ”አለ እስንድር በልቡ...

💥ይቀጥላል💥
👍1