አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
571 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
ከመሐል ይጠፋም ። የቀትር ቡናዋን እያፈላች በሸርሙጦች ተከባ ውቃቢዋን ስትለማመን ንግግር መክፈቻዎ ይኽው ነው ።

አይ ዘመን ስንቱ አለፈ ቡና ቤቱ እንዲህ እንዳሁኑ ሳይደራጅ ሠራተኛ ሠፈር ትንሽ ኪዮስክ ከፍቼ ነበር የጀመርኩት ታዲያ ያኔ ስንቱን ባላገር ገራሁት መሰላችሁ ! መቼም የሰው ነጭ ነው ያየሁበት ። ፍቅር በድርያ የሚያዝ ቢሆን ቀልጬ እቀር ነበር። እበስኩ ! ዕረፍት ሳላገኝ ነበር የምውለው ። ታዲያ በጥም ትዝ የሚሉኝ ገና ልጅነታቸውን ያልጨረሱ ተማሪዎች ናቸው በምሽት ተሰርቀው ብቅ ይሉና ድንግላቸውን አስረክበው ይመለሳሉ ። ምን የመሰሉ ሎጋዎች ነበሩ ! ”

አንዴ ከጀመረች ማቆሚያ የላትም ። ዐይኗ ዕንባ እስኪያቅር ድረስ የጥንት ኑሮዋ ውስጥ ሰምጣ ትቀራለች ። በዚህ
ጊዜ ብርቅሽ በልቧ ትቀናለች ።

ምነው ፈዘዝሽ?” አላት እስክንድር በሐሳብ ጭልጥ ብላ መሔዷን እያየ ።

መፍዘዝ ሆሆይ ! እንኳን ፈዘን ቀልጥፈንም አልሆነልን” ስትል አቤል ተመልሶ መጥቶ አጠገባቸው ተቀመጠ ።

ኖር ብላናል ” አለችው ፡ ሞቅ ካለ ፈገግታ ጋር ።

ስትሥቅ ድዷ ይታያል ። የላይኛው ድዷን ጉራማይሌ ተነቅሳዋለች ። አንገቷ ንቅሳት ድዷ ንቅሳት አቤል ያሤሩበትን አላወቀም የተከፈተለትን ሦስተኛ ቢራ ልጠጣው
ወይስ አልጠጣው በሚል ስሜት ዝም ብሎ ተመለከተው ።

“ ይሄ ነገር ቢበቃኝስ ?” ሲላቸው ፥ ምላሱ ትንሽ ትንሽ መተሳሰር ጀምሯል ።

“ እረ ጠጣ ! ምን እንዳይልህ ? ዕረፍታችሁ አይደለም እንዴ ? ” አለችው ብርቅነሽ ፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ዐይን
ልዐይን ተያዩ ።

“ ስሚ ብርቅነሽ ' ይህ ሁሉ ንቅሳት ምንድነው ?”አላት እስክንድር፡ ጣልቃ ገብቶ ። ለለከፋ መሆኑ ገብቷታል ።

ጌጥ ነዋ ! ምን አገባህ አንተ ደግሞ ? ”

“ ማለቴ ' አዲስ አበባ ስትገቢ ልታጠፊው አልሞከርሽም ? ”

ውይ ፥ ለምን ብዬ ! ቁምጥና መሰለህ ? ”

“ እሱን ተይው የሚቻል ቢሆን ኖሮ ሴቶች ንቅሳታችሁን ለማጥፋት የማትገቡበት ጉድጓድ አልነበረም ። ለመሆኑ ከሀገርሽ ከወጣሽ ስንት ጊዜ ሆነሽ ?

💥ይቀጥላል💥
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_አስራ_ስምንት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

.....በሐረርጌ ክፍለ ሀገር፤ በሀረር ከተማ ነዋሪ የሆኑት ፊታውራሪ በላይ እንግዳ፤ ከመጀመሪያ የህግ ባለቤታቸው ከወ/ሮ አይኔአበባ ጥሩነህ ከወለዷቸው ስምንት ልጆች ውስጥ፣ ብሩክ በላይ አራተኛ ልጅ ነው።
ፊውታራሪ በላይ፤ ልጃቸው ብሩክ ! በእናቱ ማህፀን ውስጥ እንዳለ፤
በወዳጅነት አብረዋቸው ደስታንና ችግርን ካሳለፉት ከባላምበራስ ትኩነህ
መብራቱ ጋር ከጓደኝነትም በላይ ወዳጅነታቸውን በጋብቻ ትስስር
ሊያሳድጉት ፈለጉና፤“ልጅህ ሴት ከሆነች ለወንድ ልጄ፤ ወንድ ከሆነ ለሴት ልጄ” በማለት ቃል ተገባቡ፡፡

ሁለቱ ጓደኛሞች፤ በእርጉዝ ሚስቶቻቸው ማኀፀን ውስጥ ባሉት ጽንሶች ሊቆራኙ በገቡት ቃል ኪዳን መሠረት፤ እንደ አጋጣሚ ሆኖ የፈታውራሪ በላይ ልጅ ወንድ ሆኖ ሲወለድ፤ የባላምባራስ ትኩነህ ልጅ ደግሞ ሴት ሆነች፡፡

በሁለቱ ሕፃናት መካከል የነበረው የዕድሜ ልዩነት ሁለት ወር ብቻ ነበር፡፡ በዚህም ብሩክ ታላቅ ለመሆን በቅቷል፡፡ በዚያን ዕለት ወንድ ተወልዶ ቢሆን ኖሮ፤ ያ ሁሉ የወላጆች ምኞት ከንቱ ሆኖ ይቀር ነበር፡፡ያ የረጅም ጊዜ ምኞታቸው ምኞት ብቻ ሆኖ ባለመቅረቱ፤ ሴቷ ልጅ
የተወለደች ዕለት የሠርግ ያክል ድግስ በሁለቱም ቤት ተደግሶ ይህችን
ዕድለኛ ልጅ በዕድሏ ብለው ሰየሟት፡፡

በዕድሏ ትኩነህና፤ ብሩክ በላይ፤ በቤተሰባቸው ፍቃድ አንዳቸው ለሌላው
የትዳር ዋልታ መሆናቸውን ሳያውቁ፤ በዚያ በወርቃማ የልጅነት ጊዜ ውሀ እየተራጩ ፤ጭቃ እያቦኩ፤ አብረው አደጉ፡፡ ብሩክና በዕድሏ በአካል እየጐለመሱ፤ በአእምሮ እየበሰሉ፤ ሲመጡ ወላጆቻቸው በትዳር እንዲተሳሰሩ የተስማሙባቸው ወደፊት ባልና ሚስትነት የታጩ መሆናቸውን ቀስ በቀስ እየተረዱ ሲመጡ፤ ለጥቂት
ጊዜም ቢሆን የመተፋፈርና፤ የመሽኮርመም፤ ፀባይ ቢያሳዩም፤ ቀስ በቀስ ይህንን እያስወገዱ፤ በተቃራኒ ጾታዎች መካከል በሚፈጠረው የግንኙነት መስመር መጓዝ ጀመሩ፡፡

ቀስ በቀስ የልጅነት ነጻ ፍቅራቸውን በጾታዊ ፍቅር እያጐለመሱት መጡ፡፡በተለይ በአንድ ትምህርት ቤት ውስጥ አብረው እየተማሩ፤አብረው እየዋሉ፤ ማምሸት ሲጀምሩ፣ ቀስ ብለው ጊዜውን ጠብቀው ሊሆን የሚችለውን፤ ከወዲሁ ቸኩለው ጀመሩት፡፡ .

በዕድሏ እዚህ ጐደለሽ የማትባል ቆንጆ ልጅ ነበረች፡፡ ምንም እንኳን የወደፊት ሚስቱ እንድትሆን በቤተሰብ መልካም ፈቃድ የተቸረችው ቢሆንም፤ የሱ፤ የግሉ፤ ብቻ መሆኗን ለማረጋገጥ ብሩክ ቀስ በቀስ እያባበለ የፍቅር ጭውውት አስጀመራት፡፡
በዕድሏ ቀስ በቀስ ከብሩክ የበለጠ በፍቅር ወደቀች፡፡ ብሩክን የምትወድበት ቃልም አልነበራትም፡፡ በአጠቃላይ ነፍሷ እስከምትወጣ ድረስ ትወደዋለች፡፡ ይወዳታል፡፡

ይህ ለሁለቱም ፍቅረኛሞች ኦቦል የሆነ ፍቅር ቀስ በቀስ ሥር እየሰደደ የሚያስቀኑ እየሆኑ ሄዱ፡፡በዚህ መሀል ነበረ እንግዲህ አብዮቱ የፈነዳው፡፡ በዚያን ጊዜ በፊታውራሪ በላይ ቤት በአሽከርነት ተቀጥሮ ይሠራ የነበረው አደፍርስ፤
በአብዮት ጥበቃ አባልነት በቀበሌ ውስጥ ከተመረጠና፤በኋላም የቀበሌው የአብዮት ጥበቃ ኃላፊ ከሆነ በኋላ፤ ያንን ለዘመናት ውስጡን ሲበላው የቆየውን የፊታውራሪን ልጅ በዕድሏን የማግኘት ሕልሙን ሊያሳካ
ቆርጦ ተነሳ፡፡

በመጀመሪያ አባቷን መሣሪያ ደብቀዋል በሚል ምክንያት ካሳስራቸው በኋላ “በሕዝብና በአብዮቱ ላይ ደባ የፈጸመ አድሃሪ ስለሆነ መረሸን አለበት” የሚል አቋም ያዘ፡፡
ለዚህ ጥቆማው ሚስጥሩን ያውቃሉ በሚል ሽፋን ካሳሰራቸው ጠቅላላ
ቤተሰቦች መካከል በዕድሏ እንዷ ነበረች፡፡

“አባትሽን ወይንስ ብሩክን?” ሲል ለህሊና የከበደ ጥያቄ አቀረበላት ።ከዱላው ብዛት የተነሳ ከሁለቱ አንዳቸውን ከመምረጧ በፊት ሁለቱንም ነበር መልሷ፡፡በመጨረሻ ላይ ግን ሰውነቷ በዱላ ብዛት ተተልትሎ
አባቷንም፤ ብሩክንም፤ እራሷንም እንዳታጣ ስለሰጋችና የሁለቱንም
ህይወት ለማትረፍ ስትል፤ ያቀረበላትን ጥያቄ! እንደኮሶ እየመራራት ለመቀበል ተገደደች፡፡

ከዚያም ብሩክ በፀረ አብዮተኛነት ስም ወህኒ ቤት እንዲገባ ካደረገ በኋላ፤
አደፍርስ ድል ያለ ድግስ ደግሶ በሠርግ አገባት፡፡
ብሩክ ከአባቱ ጋር እሥር ቤት ውስጥ እንዳለ፤ አደፍርስ እና በዕድሏ
መጋባታቸውን ሲሰማ እራሱን ጠላ፡፡
መፈጠሩን አማረረ፡፡ በእንባ እየታጠበ ፤ አንጀቱ እየከሰለ! የሚወዳት የሚያፈቅራት ከጭቃ ማቡካት ጀምሮ በልቡ ውስጥ የጠነሰሳት ፍቅረኛውን መነጠቁን አመነ፡፡
ለስድስት ወራት ያህል በዚህ ሁኔታ በእሥር ቤት እንዲቆይ ከተደረገ
በኋላ ተሳትፎው በንባብ ደረጃ ብቻ ስለሆነ “ማሪኝ አብዮቴ” የሚል
መዝሙር ዘምረው በምህረት እንዲለቀቁ ከተደረጉት ወጣቶች መካከል አንዱ ለመሆን በቃ፡፡

የአደፍርስ ምኞት እንዲገደል ነበር፡፡ ሳይሆንላት ቀረ፡፡

“ብሩክ ምን ለመሆን ነው የምትፈልገው? “ ሲሉት አባቱ..
“ዶክተር፧ ኢንጂነር፣ አውሮፕላን ነጂ፣ሳይንቲስት ” ጥሩ ጥሩውን ሁሉ
ለመሆን የሚመኘው፤ በትምህርቱ ጠንካራ የነበረው ልጅ ሞራሉ ተነካ፡፡
ደስታን አጣት :: ከዚያም አሥራ ሁለተኛ ክፍልን እንደጨረሰ በቀጥታ በፖሊስ መኮንኖች ማሰልጠኛ ኮሌጅ ገባ፡፡
በማሰልጠኛው ውስጥ ባስመዘገበው ከፍተኛ ውጤት ልዩ ሽልማትን ለማግኘት የበቃ ጠንካራ ተማሪም ነበር፡፡ ትኩረቱን ሁሉ በማስልጠኛው በሚሰጠው ትምህርት ላይ አደረገ፡፡ በዕድሏን አጥቷታል ፤ስለፍቅር የምትዘፍን ልቡ በዚያ ምትክ ለዘመናት የሀዘን እንጉርጉሮ ስታንጐራጉር ኖራለች፤ ስለፍቅር መስማት ይጓጉ የነበሩ ጆሮዎቹ ያንን ሲሸሹ ኖረዋል
በለጋነቱ በውስጡ የደረቀች የፍቅር አበባ ሁሉን እንዲጠላ አድርጋዋለችና እልሁን የሚወጣው ጠንክሮ በመስራት ብቻ ሆነ፡፡

የሚያዳምጠው ማንኛውም የፍቅር ዘፈን ስንኝ ለሱ መሪር የሀዘን ስሜቱን እያጫረበት በዕድሏን በዓይነ ህሊናው የእንባ ጭጋግ ከጋረዳቸው ዐይኖቹ ባሻገር በትዝታና በሰቀቀን እያሰባት፤ ረጅሙን ጊዜ በብቸኝነትና በሃዘን አሳለፈው፡፡

በዕድሏ የሶስት ልጆች እናት ስትሆን፤ እሱ ግን ይኸውና እስከ ዛሬ ድረስ የትዳርን ነገር ሳይመኘው፤ ሳያስበው በአደፍርስ ላይም የቂም በቀል እጁን ሳይሰነዝር፤ የራሱን ዓለም በራሱ ውስጥ ፈጥሮ በመኖር ላይ ይገኛል፡፡

ሻምበል ብሩክ በመ/ቤቱ ውስጥ ተወዳጅና ተሰሚነት ያለው ወጣት መኮንን ነው።በአጭር ግዚው ውስጥ የሹመት ባለ ዕድል ለመሆን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በማታው መርሃ ግብር፤ በማኔጅመንት ለዲግሪ በመማር ላይ ይገኛል፡፡

ሻምበል የቤት ሠራተኛ ቀጥሮ ሁለት ታናናሽ ወንድሞቹን በማስተማር ላይ ሲሆን፤ በትዳር ላይ የነበረው ምኞት ገና በአፍላው ከተጨናገፈ አስቦትም፤ አልሞትም አያውቅም፡፡ እሱ
አይጨነቅበት፤ እንጂ የትዳር አምላክ እራሱ ለሱ ሲጨነቅለት፤ ሲጠበብለት፤ ቆይቶ የሚሆነውን ሊሰጠው ፤ በሀዘን የተሰበረ ልቡን ሊጠግንለት፤ ተቃርቧል፡፡

በቢሮው ውስጥ ወንድሟን ልታስፈታ ለአቤቱታ የገባችውን ወጣት ሲያይ፤ እንደዚያ በድንጋጤ ደንዝዞና፤ ፈዝዞ፧ የቀረው ያለምክንያት አልነበረም፡፡
ያች ወጣት፤ ያች ውብ ልጃገረድ፤ ሞቶ አፈር የለበዕ ስሜቱን የቀሰቀሰችበትን፤ የሻረ የልቡን የውስጥ ቁስል የነካካችበት፤ ያለምክንያት አልነበረም፡፡ በዚያች ቅጽበት ሻምበል ብሩክ የልጅነት እጮኛው፤ ከሁሉም በላይ የሚያፈቅራት ጓደኛው፤ በዕድሏ እራሷ የመጣች ነበር የመሰለው
በጣም ነው በመልክ የሚቀራረቡት፡፡

ሁለመናው ተረብሾ፤ ያችን ወጣት ለማነጋገር አንደበት ልሳኑ የተዘጋው፤ በዚህ ምክንያት ነበር በተለይ ዓይኖቿ ቁርጥ በዕድሏን ናቸው ለወንድሟ ዋስ ሊሆንላት ቃል ሲገባላት ያቺ ወጣት በኑሮ
ውጣ ውረድ ምክንያት የደረሰባትን
👍3
ችግር፤ አባቷን በጦርነት ምክንያት
ማጣቷን፤ እናቷ በሕመም ስቃይ የአልጋ ቁራኛ መሆኗን፤ የምትወደው ወንድሟ ደግሞ ፀባዩ እየተለወጠ ሄዶ እስከመታሰር የደረሰበትን ምክንያት፤ በዚያች አጭር ጊዜ ውስጥ አጫወተችው።

በዚያን ጊዜ ልቡ አዘነላት ከሀዘኔታውም ውስጥ አብሯት በስሜት አለቀሰ ፡፡ ለምን የዚያን ቀን ምሽት በሕልሙ መጣችበት? እንጃ ! ሻምበል ብሩክ በዕድሏን በትህትና ውስጥ ስላየ ትህትና የበለጠ ናፈቀችው፡፡
ከአሁን አሁን ስልክ ትደውላለች ብሉ ጆሮዎቹን በቤቱም፤ በቢሮውም፤
ስልክ ላይ ጥሎ ሲያዳምጥ ዋለ፡፡ አልደወለችም፡፡ በሁለተኛውም፤ በሶስተኛውም ፤ በአራተኛውም ቀን ሳትደውል ቀረች፡፡ ተጨነቀ፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ እየናፈቀችው ነው፡፡

ለሴት ልጅ የነበረው የቀዘቀዘ ስሜት በዚህች ወጣት ምክንያት ለምን ተቀሰቀሰ? ትህትና.....ትህትና...ትህትና...
በሀሳብ ታየችው፡፡ስታለቅስ፤ አቤት አይኖቿ ሲያሳዝኑ፤ ስትናገር ልሳኗ የሚጣፍጥ፤ቅልስልስ ስትል፤ እንዴት ያምርባታል!፡፡ ከዚያም ዐይኖቻቸው በድንገት ሲጋጩ ከድንጋጤዋ ውስጥ ዘልቆ ከዐይኖቿ ውስጥ ያነበበው ስሜት
እንዴት ነበር?፡፡ በጣም ደስ የሚል ፤ ልዩ ስሜት ነበር፡፡ ቃላት ሊገልጹት የማይችሉት ስሜት.....
ይህ ሁሉ በሀሳቡ እየተመላለሰ፤ ሻምበል ብሩክ ትህትናን በመናፈቅ የሚሆነውነ አጣ፡፡ ዋስ ሆኖ ወንድሟን አስፈታላት እንጂ ከወንጀሉ ነፃ ሆኖ አልተሰናበተም፡፡ ጉዳዩ ያላለቀ በመሆኑ መፈለግም ሊኖር
ይችላል፡፡ታዲያ ምነው ድምጿን አጠፋች? ሁኔታው ግራ አጋብቶት ከረመ፡፡

ሻምበል ብሩክ በሥራ ላይ አምሽቶ መግባቱ ነው፡፡ ከምሽቱ አንድ ሰዓት
ተኩል ሲሆን ከቤት ደረሰ፡፡ ከዚያም ከታናናሽ ወንድሞቹ ጋር ቼዝ እየተጫወተ ሳለ የቤቱ ስልከ የጥሪ ድምጽ ሰጠ :: የአሥራ አራት ዓመት ዕድሜ ያለው ትንሽ ወንድሙ ፀጋዬ ሄዶ ስልኩን አነሳ፡፡
“ ሀሎ" አለ ፀጋዬ፡፡

“ሀሎ” አለው ከወዲያ ማዶ ያለው ቆንጆ የሴት ድምጽ፡፡
“ማን ልበል ?" ፀጋዬ አዲስ በሰማው ድምጽ ግራ ተጋብቶ፡፡
“ሻምበል ብሩክ ቤት ነው?"
አዎን”
ይኖራሉ ? ”
"አሉ” አላት፡፡
“እባክህ አቅርብልኝ ?"

ጋሼ ስልክ ይፈልግሀል” አለውና ስልኩን አስቀምጦ ተመለሰ፡፡ ሻምበል ብሩክ በልቡ ምን አለበት እሷ ብትሆን? ወይኔ ብሩክ እባክህን እሷን አድርግልኝ” እያለ፤ እሷን እንዲያደርግለት እየተመኘ፤ ወደ ስልኩ ሄደና አነሳው፡፡

“ሀሎ "አለ ልቡ እየዘዘለች፡፡
“ሻምበል ብሩክ ነህ”
“አዎን ነኝ ማን ልበል?፡፡ ተመስገን አምላኬ፡፡ አዎን አሷው ናት!”

" ትህትና እባላለሁ፡፡ ካልረሳኸኝ” ሻምበል ብሩክ ብቻውን ቢሆን ኖሮ በደስታ ይጨፍር ነበር፡፡ ምን ያደርጋል? እዚያ ወዲያ ወንድሞቹ አሉ።ያዩታል፡፡ የሚይዝ የሚጨብጠው ጠፍቶት ተቁነጠነጠ፡፡

"ትህትና ምነው እስከዛሬ ድረስ ሳትደውይልኝ?”
"አልተመቸኝም ነበር ሻምበል”
“ በጣም እንደናፈቅሽኝስ ይገባሻል?"
እንዴት ማወቅ እችላላሁ ሻምበል?" በልቧግን“ እኔም ተቃጥዬልሃለሁ” እያለች ነበር፡፡

እኔ እንጃ ብቻ ስንገናኝ ብነግርሽ ይሻላል፡፡ ሰሞኑን ጆሮዬ ከኔ ጋር ሳይሆን ከስልኮቹ ጋር ነበር የከረመው፡፡ ለማንኛውም ከስልክ ይልቅ በአካል ተገናኝቶ መጫወቱ አይሻልም? ሲላት....
“ አዎን እንደሱ ይሻላል” አለችው ቶሎ ብላ፡፡

“ እናትሽ ተሻላቸው ትህትና? አንዱ አለምስ ፀባዩን አሻሻለ?”

“ እማዬ እየተሻላት ነው፡፡ ደህና ነች :: አንዱዓለሜ እንዴት ተለውጧል መሰለህ? በዚያች እሥር ቤታችሁ ውስጥ ምን እንዳቀመሳችሁት እንጃ፡፡” እየሳቀች፡፡

እስቲ ስለሁሉም ለመጫወት መቼ እንገናኝ ታዲያ? እኔ እንዳልደውልልሽ እኮ ስልክ የለኝም ስላልሽ ነው እንጂ ይሄን ያህል አልጨክንም ነበር” በማለት አንጀቷን ሊበላው ሲሞክር.....

“ ሻምበል እኔንም እንደጨካኝ አትቁጠረኝ፡፡ ያለመመቸት ጉዳይ ነው፡፡”
በልቧ ግን ነገ አይመቸኝም ካለ ጉድ ፈላ! ከዚህ በላይስ መቆየት አልችልም” እያለች ነበር፡፡

ዛሬ መሽቷል እንጂ ዛሬ ብንገናኝ ደስ ይለኝ ነበር” ሳታስበው አመለጣት፡፡

ሻምበል ጆሮውን ማመን አቃተው፡፡
“ ለምን ነገ አንገናኝም ታዲያ?” አላት በጉጉት፡፡ደስ ይለኛል” እንዲህ በድፍረት ስሜቷን ሳትደብቅ እንድትናገር
የገፋፋት የቀመሰችው አልኮል መሆኑን አላወቀም፡፡ የሚገናኙበትን

ሰዓትና ቦታ ተቀጣጥረው! ትንሽ ተሳስቀው በናፍቆት ተሰነባብተው ፤
ስልኩ ተዘጋ፡፡
ሁለቱም ልባቸው በናፍቆት ተሸብሮ፤ የዛሬው ምሽት ከድንጋይ እየከበዳቸው ተለያዩ፡፡ እውነትም ያ ምሽት በዕድሜአቸው ሙሉ ከሚያውቋቸው ምሽቶች በጣም ረጅሙ ምሽት ነበር፡፡
እንደዚያ ከሻምበል ብሩክ ጋር በስልክ ስትጨዋወት አዜብ ከፊት ለፊቷ
ቁጭ ብላ በዐይኖቿም፤በእጆቿም፤ በጥርሶቿም ጭምር አመራር
እየሰጠቻት ነበር፡፡
ስልኩ ከተዘጋ በኋላ ሻምበል ብሩክ ከአምስት ቀን በፊት ወዳያት ወደ
ትህትና ሲዘምት፤ እሷም ከአምስት ቀናት በፊት ለመጀመሪያ ጊዜ ልቧን ውሃ ወዳደረገው መልክ መልካም ወጣት በሀሳብ ከነፈች.....
ሁለቱም በስሜት እየተፈላለጉ በመንፈስ እየተደባበሱ... አካላቸውን በየአልጋቸው ላይ አሳረፋ፡፡ ትህትና እንደዚሁ እየቃዠች፤ የነገው ቀጠሮ እንደናፈቃት፤ እናቷን እቅፍ አድርጋ! ተኛች፡፡
ሻምበል ብሩክ ግን እንቅልፍ እምቢ ስላለው መጽሐፍ ማንበብ ፈለገና
ያንን ከዚህ በፊት አላነብም ብሎ ያስቀመጠውን የፍቅር መጽሐፍ ለማንበብ ጉጉት አድሮበት “ሀ ”ብሎ ገጹን ገለጠ....

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2
አትሮኖስ pinned «#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ ፡ ፡ #ክፍል_አስራ_ስምንት ፡ ፡ #ድርሰት_በትክክል_ገና .....በሐረርጌ ክፍለ ሀገር፤ በሀረር ከተማ ነዋሪ የሆኑት ፊታውራሪ በላይ እንግዳ፤ ከመጀመሪያ የህግ ባለቤታቸው ከወ/ሮ አይኔአበባ ጥሩነህ ከወለዷቸው ስምንት ልጆች ውስጥ፣ ብሩክ በላይ አራተኛ ልጅ ነው። ፊውታራሪ በላይ፤ ልጃቸው ብሩክ ! በእናቱ ማህፀን ውስጥ እንዳለ፤ በወዳጅነት አብረዋቸው ደስታንና ችግርን ካሳለፉት…»
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

....“ ምናገባህ ? ሞዛዛ ?" ስትለው ድምጿ የብሽቀት ቅላጺ ነበረው ።

“እውነት ብርቄ ፥ ምን ያህል ጊዜ ሆነሽ?” አላት ሳምሶን?

"አራት ዓመት!”

"የአራት ዓመት የሥራ ልምድ ! ከሌሎቹ አንጻር ሲታይ ትንሽ ነው ” እላት ሳምሶን "

“ መላጣ ! ” አለችው ፡ ጭንቅላቱን በዐይኗ ቂጥ እያየችው ።

“ በአራት ዓመት ውስጥ ስምሽን ለመለወጥ አልሞክርሽም ? ”አላት እስክንድር ሲቀልድባት ፡ “ እዲስ የከተማ
ስም እንደ ራሄል ኤደን ማርታ ፡ ዓለም ከተሜ ለመሆን እ ? ”

“ሒድ'ደረቅ ! ”

ሒድ፡ደረቅ !ሒድ፡ደረቅ!ደረቅ ማርታ በቅናት ቅንድቧን እያርገበገበች ከፊቱ ድቅን አለችበት ። በሐሳቡ ቁመናዋን ቃኘ በሞቅታ መንፈስ እንደገና አለማት ፡ ኪሱ ባዶ ማለም ብቻ ! ማነጣጠር ብቻ !

"ሒድ ፡ ደረቅ የሴቶች የጋራ ፈሊጽ ” አለ በልቡ ።

የብርቅነሽ ጥሬነት አስገረመው ፡ ስትጫወት የባላገር ለዛ አላት ። ንቅሳቷ ባላገርነቷን ይመሰክራል የባላገር ስሟን
አልለወጠችም " እምብዛም የከተሜ ጭምብል አላጠለቀችም ግን ከሀገርሽ ለምን ወጣሽ ? ” አላት በድንገት ።

“ ሆሆይ !ጋዜጠኛ ነህ እንዴ ?”

ባልሆን ፥ ይህን ሥራ ምን አስመረጠሽ ፡ ማለቴ ነው ። ””

“ ዋ ! ወድጄን መሰለህ ? ግድ ሆኖብኝ እንጂ ” ከማለቷ ፊቷ የኀዘን ጭጋግ ለበሰ

“ ምነው ?እንዴ? ” አላት እስክንድር ስሜቷን ተከትሎ ስሜቱ እየዳመነ።

“ ባልተቤቴ ነው ለነዚ ያበቃኝ ! በሱ ምክንያት ነው ሀገሬን ለቅቄ የወጣሁት እያለች የታሪኳ ዳር ዳር ጨረፈችው
በፍቅር ለቀረባት ሁሉ ታሪኳን ታወራለች
ልስ ልስ ሆኖ ለቀረባት የአንጀቷን ትዘከዝካለች የተማረ መስሎ ለታያት ችግሯን አፍረጥርጣ ትናገራለች ። መፍትሔ ይገኝልኛል ብላ አይደለም :: የውስጧን ተንፍሳ ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን የመንፈስ እረፍት ታገኛለች።

«« እባክሽ አታጓጊን ፣ በደንብ አጫውቺን" አላት እስክንድር ታሪኳን ለመስማት ተጣድፎ።

“ አያችሁ እናንተ ዕድለኞች ናችሁ : ከደኅና ቤተሰብ በመወለዳችሁ ወይም ከተማ በማደጋችሁ ለመማር በቅታችሆል እኔ የቀለም ትምህርት የለኝም ማንበብና መፃፍ እንኳ የቻልኩት አሁን የመሰረተ ትምህርት ዘመቻ ከተጀመረ ወዲህ ነው።
የድሀ ገበሬ ልጅ ነኝ ። ያውም በእንጀራ
እናት ያደግኩ !ህም እቴ! ታድያ በአሥራ አራት ዓመቴ ተዳርኩ ። ባሌ ገበሬ ነበር ። እኔ ሁለተኛ ሚስቱ ነኝ ።የመጀመሪያ ሚስቱ ከተጋቡ መንፈቅ እንኳ ሳይሞላቸው ሞታበት ነበር ። ወላጆቼም ሲድሩኝ ይህን ያቃሉ በእድሜ በሰል ያለ ነው ። ጸባዩም ጥሩ ነው ለትዳሩ ታታሪ ነው ” ተባለና ተሰጠሁ ።

“ ጎጆአችንን እያሞቅን ፡ የባላባቶችን ግልምጫና ዱላ በጋራ እየተቀበልን መኖር ጀመርን ፡ ምን ይሆናል ። እግዜር ለትንኮሉ ማሕፀኔን ድፍን እደረገው። ዓመት ጠበቅን ሁለት ዓመት ጠበቅን ልጅ የለም ። በእኔና በባልተቤቴ መሐል ቅሬታ መጣ ያም ሆኖ አልተቃቃርንም ። ድህነት ያስተሳስረን ነበር ። እሱ ከገበሬዎቹ ጋር ውጭ ደክሞ ውሎ ሲመጣ ከቤት ያለሁ
ረዳቱ እኔው ነበርኩ በባላባት ጅራፍ ጀርባው ቆስሎ ሲመጣ አንጀቴ እየተንሰፈሰፈ የማለቅስላት እኔ ነበርኩ ዋ! እቴ ምን ያደርጋል!

እንዲህ እንዲህ እያልን አምስት ዓመት ያህል እንደኖርን አብዮቱ ፈነዳ ። ለውጥ መጣ ። ደክመን ለባላበት መገበሩ ቀረ። እፎይ አለን ። ቤታችን ሙሉ ሆነ እውነቴን ነው ደህና ነገር መብላት መልበስም ጀመርን ። ምን ይሆናል ። ከድህና
ኑሮ ጋር ተያይዞ ነገር መጣ ባልተቤቴ ሌላ ሴት ጋር በስርቆት መሔድ ጀምሯል የሚል ወሬ ሰማሁ ። ስውል ሳድር እኔም
ነገሩን ደረስኩበት። እንዲያውም አንድ ልጅ እንደ ወለደችለት አረጋገጥኩ ። ቀናሁ ! ቅናት አንገበገበኝ ። በሐሳብ
ተብከነከንኩ። ጨስኩ ።ቤት ውስጥ !
መቀመጥ አቃተኝ ብዙም ሳልቆይ ጓዝ ምንጓዝ ሳልል በርሬ ወጥቼ አዲስ አበባ ገበኋት !

“ እዚህ ስደርስ ደግሞ ያዘጋጀሁት ማረፊያ የለኝ ፥ እንደሁ ሜዳ ቀረሁ ። ትንሽ ቀን ሰንብቼ በደላላ አማካይነት
ግርድና ተቀጠርኩ። ስድስት ወር እንደ ሰራሁ ግርድናን እርም ብዬ ተውኩት። አባስኩ እቴ ! የሰው ቤት ሹሮ ሲያልቅ
እኔ ላይ ማፍጠጥ ። ዕቃ ሲጠፉ እኔን መወንጀል ። ምነው ከዚህ ሁሉ ሥጋዬን ሸጨ ባድር አልኩና ሽርሙጥና ጀመርኩ
እላችኋለሁ ።

ብርቅነሽ ስትናገር ታላቅ ማዕበል ተነሥቶ ባሕር ውስጥ የከታቸውን ያኸል ሥስቱም ጸጥ ብለው ነበር ። አሳዘነቻቸው። ምስኪን ጥሬ ፍጥረት ! በመጠጥ ሞቅታ ኃይል ለሁሉ ነገር ግዴለሽ ሆኖ የቆየው አቤል እንኳ፥ ከብርቅነሽ አፍ የድህነት ድምፅ ሲሰማ ቸል ማለት አልቻለም ። ሕዋሳቱ በኀዘን ስሜት ተወራጩ ::

ግን ዝዎም ብለሽ ከምትኮበልይ ፥ ሰላምን በአካባቢሽ በሚገኘው የሴቶች ወይም የገበሬ ማኅበር አመልክተሽ መፍ
ትሔ ኣትፈልጊም ነበር ? ” እላት እስክንድር ፡ ከማዘኑ የተነሣ የሚናገረው ጠፍቶት ።

ዋ እቴ ! ቤት ከፈረሰ ወዲያ ሁሉስ ምን ሊበጅ ? አየህ ፡ ቅናት ከመጣ ቤት ፈረሰ ማለት ነው። ለሁሉም እኔ ለማንም አላማከርኩ ። የሚያለቅሱ ልጆች የሉኝ ' ነጠላ ሰው ምናለበት አልኩና ብር ብዬ አዲስ አበባ ፣ ”

ታዲያ ባልሽ ሊፈልግሽ አልመጣም ” አላትአቤል በሁኔታዋ ስሜቱ ተነክቶ ።

“ ውእእይ • ሥራ አጥቶ ! እንዲያውም ከዚያ ሀገር ለንፀግድ የሚመላለሱ ሰዎች እዚሁ ቡና ቤት አግኝቼ ሲነግሩኝ' ውሽማውን ጠቅልሎ ይዟል አሉኝ • እዩዬ ! ” ብላ ሳትጨርስ ጥሬ ሰማች «

“ ብርቅነሽ ? ! አንቺን'ኮ ነው ? ” የቡና ቤት ባለቢቷ ድምፅ ነበር
“ እመት ! ወይ ጕዱ ዛሬ ! ” እያለች ብርቅነሽ ከተቀመጠችበት ተነሣች

“ እንድዩ ! ሰው ሲገባ አትታዘዥም እንዴ! ምን ይጎልትሻል ? ”

ብርቅነሽ የውስጧን ተንፍሳ ቃጠሎዎን አብርዳ ተነሣች ፡ እስክንድር ተከዘ ቃጠሉዋ ወደ እሱ ተላለፈበት ኀዘኗ ጠልቆ ወጋው ። ቅናት ተፈጥሮአዊ ነው ሀብታምና ድሀ አይልም ። የወደደ ሁሌ ለወደደው ነገር ይቀናል ። ለቀናበት ነገር ይሠዋል ። ብርቅነሽ የቅናትን እሳት ሸሽታ ኮበለለች ። ከቅናት ሸሽታ ሴትኛ አዳሪ ሆነች "

እስክንድር ሐሳቡ ከግላዊነት ወደነማኅበራዊነት መጠቀ ለእሱ ሲጋራ መግዣ መስጠት ያቃታቸው ደሀ እናቱ ላይ ሆኑ፡ሕዝቧን በሰፊው ማስተማር ' በቂ ኢንዱስትሪ ከፍታ እነብርቅነሽን ማሠማራት ያልቻለች ረሀብን ለማጥፋት
ማይምነትን ለማጥፋት ርካሽ ልምዶችን ለማስወገድ በባህል ለማደግና የቴክኖሎጂ ውጤት ተጠቃሚ ለመሆን የልጆቿን እጅ የምትማጠን እናት ሀገር፡እጆቿን ዘርግታ በሐሳቡ ታየችው
ከሐሳቡ ፋታ አግኝቶ እሱነቱን ወዳለበት ሲመልስ ምሶን ዐይኑን አፍጥጦ ተመለከተ ።አስተያየቱ አላማረውም ። በልቡ ምርምርህን እዚያው ዩኒቨርስቲው ውስጥ አድርገው ፥ ይሄ መጠጥ ቤት ነው የሚለው መሰለው "
እና እስክንድር ብርጭቆውን አነሣ መጠጣት ! ለጊዜውም ቢሆን ራስንም አካባቢንም ለመርሳት ህሊናን ለማዘናጋት
መጠጣት!

“ ስማ እንጂ እስክንድር እየመሸ ኮ ነው ! ” አለው ሳምሶን ዐይኑን አጉረጥርጦ "

“ እ ? እሺ • እንሒድ እንዴ ? ”

ሁለቱም ብርጭቆአቸውን አጋብተው ብርቅነሽ እስክትመለስ ጠበቁ አቤል ሶስተኛው ቢራ ላይ በግማሽ ተሸንፏል።

የብርቅነሽም ልብ ከእነሱው ጨዋታ ጋር ቀርቶ ስለ ነበር የታዘዘችውን በፍጥነት አቀራርባ ተመለሰች "

“ መሔዳችን ነው እንግዲህ ” አላት እስክንድር ለመነሣት እየተንጠራራ ።

“ ተጫወቱ እንጂ 'ምነው ? ” አለች' አቤል አጠገብ እየተቀመጠች ።

“ እንሒድ እባክሽ ! ገና መውደቂያችንንም አላዘጋጋጀን ” አላትና “ አንቺም ከሦስታችን አንዳችንን ይዘሽ ማደር አለብሽ ” አላት ።

ከሦስታችሁ በዕድሜ ልጅ የሆነውን ነው የምፈልገው ።

“ እንዴት ታውቂያለሽ? ግንባራችን ላይ አልተጻፈ!”

ውይ በደንብ ያስታውቃል አሁን ለምሳሌ እሱ በዕድሜ ልጅ ነው ” አለች አቤልን እንደ ማቀፍ ክንዷን ትከሻው ላይ ጣል አድርጋ ። “ ሳምሶንም ሰውነቱ ፋፋ
እንጂ ጢም እንኳ የለውም ። ባንዴ የተመዘዘ ሰውነት መሆኑ ያስታውቃል ።
እናትሽን ! ” አላት ሳምሶን ሣቅ አፍኖት ።
“ በይ ቀጥዪ እኔስ ?” አላት እስክንድር

“ አንተ እንኳ ጠንዝተሃል ፡ ታስታውቃለህ ” አለችው እየሣቀች።

“ ያጠንዛሽ ! ” አለ እስክንድር ፥ በልቡ እየሳቀ ወደ አቢል ጆሮ ተጠግቶ ፥
ከእንግዲህ የካምፓስ ፖሊሶች አያስገቡንም።መሽቷል።እዚሁ ከብርቅነሽ ጋር ማደርህ ነው” አለው ።

አቤል በቋንቋ መልስ መስጠት አልቻለም በእሺታ ቅንድቡን ሽቅብ ቀልሶ ፈቃደኛነቱን ገለጸ። ፍላጎቱ አለው ።
ግን እንዴት ይሆናል ? ያለ ገንዘብ ይታደራል እንዴ ?

አይዞህ " ችግር የለም ” አለው ሳምሶን ግር እንዳለው አይቶ ።

አቤል በአልኮል የደከሙ ዕይኖቹን እንደገና አስለምልሞ በእሺታ ግንባሩን ነቀነቀ።

የአቤል የደከመ ገጽታ እስክንድር ላይ አንዳች የሀዘን ስሜት ፈጠረበት ። ለእምነቱ ግትር የነበረው አቤል ክፉኛ እየተረታ መምጣቱን ገመተ። እነሆ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሴት ጋር ውጭ ለማደር ፈቃደኛ ሆነ ።.ሴት ልጅ ክንዷን
ትከሻው ላይ ስታደርግ ወይም ስታቅፈው ተቃውሞ አላሳየም ። በዚች ቡና ቤት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለ ትዕግሥት ከአፉ አውጥቶ ተናገረ ። በእምነት ግትርነት ተወጣጥሮ የቆየ እሱነቱ ሳላ : ይህ መጠጡ የፈጠረው የአካል ድካም ብቻ አይደለም ፤ የመንፈስ መድከም ነው መንፈስ ሲደክም ደግሞ አካልም ይዝላል ምላስም ይተሳሰራል ሰውነት ከአድራጊነት ወደ ተመልካችነት ወይም ታዛቢነት ይሸጋገራል ።

እስክንድር በልቡ ይህን እያሰበ '' ታዲያ አቤል ጓደኛዬ መንፈሱ ሲደክም፡ በማበረታታትና የቀድሞ እምነቱን
በመጠበቅ ፈንታ' ሲሸሸው ወደ ቆየው ተግባር መጨመሩ ትክክል ነው ? ” ሲል ራሱን ጠየቀ ።


ያስፈልጋል : አንዳንዴ ራስን መርሳት ያስፈልጋል ሁልጊዜ ራስን አስታውሶ እንደ ምን ይቻላል? አቤልም ዛሬ ራሱን ይርሳ ! እርሱነቱን በተለየ ገጽታው ይመልከተው ።
ሕይወት ዥጉርጉር ናት ” እያለ ሲያስብ ፡ አልኮል የማይበግረው ኅሊናው ጦሩን መዝዞ ተነሣበት ። እስክንድርም
ጋሻ ይሆነው ዘንድ የቢራ ጠርሙሱን አነሣ ። ነገር ግን ጨርሱ ባዶ ነበር ።

“ እንሂድ እንጂ መኝታ ከያዝን በኋ ከፈለግክ ሌላ ጋር እንጠጣለን አለው ሳምሶን በቁጣ ድምፅ።

ወዲያው ሂሳቡን ክፍሎ ተነሣና ብርቅነሽን ጠቀሳት ። እስከ ውጭ በር ተከተለችው ። ገንዘብ በእጅዋ ሲያስጨብጣት “ ዋ ! ልጁ ምንም አያቅም ብለሽ
እንዳትፈነግይው ” ሲል አስጠነቀቃት ።

“ እኔ ብርቅነሽ ? ሥራዬም አይድል ። ይልቅ ቻው ! ”ብላው ገባች።

እስክንድር ከአቤል ጋር ጠዋት ጆሊ ባር ለመግናኘት ቀጠሮ ሰቶት ወጣ።

ሳምሶን ብቻ ዛሬ በረንዳ እንዳናድር
አለው እስክድር በስሥጋት ።

"ግድ የለህም፥ ገና ሰዓት አለን አለ ሳምሶን ፥ ፊት ለፊት እየቀደመ።

ሁለቱ ከሔዱ በኋላ'አቤልና ብርቅነሽ ተፋጠው ቁጭ ሆነ ከመሐከላቸው ቃል የሚተነፍስ ጠፋ ። ብርቅነሽ ዐልፎ ዐልፎ “ ተጫወት እንጂ ” እያለች ብትጎተጉተውም አቤል ምላሱ ሊፍታታለት አልቻሉም ። ወንድ ሴት
ልጅን ምን እያለ ማጫወት እንዳለበት ገና አላወቀም ።

ወይም መኝታ ክፍልህን ላሳይህ ? ዐረፍ የምትል ከሆነ አለችው ።

“ ብቻዬን ? አላት ድምፁ በመጠጡም በፍርሀትም ተወላግዶ

“አይይ እኔም እመጣለሁ ነገር ግን ከአምስት ሰዓት ተኩል በፊት ሥራ ለመፃቆም ባለበትየዋ አትፈቅድልኝም
እስከዚያ ድረስ እንተ ገብተህ ዐረፍ በል ” አለችው እየሣቀች።

“እሺ በይ አሳዪኝ ። ”

ከቡና ቤቱ በስተጀርባ ከሚገኝ አንድ ክፍል ውስጥ አስገብታው ተመለሰች "
አቤል ቶሎ ልብሱን አላወለቀም አልጋው ላይ ተቀምጦ ጣራ ግድግዳውን ይመለከት ጀመር ። አልጋው ገና
ቁጭ ሲልበት እሮሮውን አሰማ እየተንቃቃ አቃሰተ ። ለዕረፍት ሳይሆን ለድሪያ የተዘጋጀ አልጋ ። ክፍሉ የቤት መልክ አልነበረውም ሆኖም አቤል ይህን ሁሉ ለማጤን አልቻለም ። እግሩን ሳያወጣ በጎኑ አልጋው ላይ ጋደም ሲል ሰማይ ምድሩ ብዥዥ አለበት ። የሚሽከረከር ወሰለው ዐይኑን ዘጋ ። አሁን ደግሞ ክፍሉ ሳይሆን የገዛ ጭንቅላቱ የሚሽከረከር መሰለው ። ብርቅነሽ በሐሳቡ መጥታ ዕርቃኗን ከፊቱ
ቆማ ብዥታውን አበረደችለት ሰውነቱ በወሲብ ግለት ተወማበጠረ ። ቸኮለ ዐይኑን ሲገልጥ ግን ከፊቱ የቆመ ነገር
አልነበረም " ወና ቤት ! ወናነቱ ያስፈራል ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ጥንድ የመሆን ተስፋ በልቡ ባይቀረጽ ኖሮ አቤል ወናውን ክፍል ሸሽቶ በፈረጠጠ ነበር ።

ወናነቱን ላለማየት ወይም ቀድሞ ያየውን እርቃን ደግሞ ለማየት እንደገና ዐይኑን ጨፈነ " የብርቅነሽ ዕርቃን በድጋሚ ሊታየው አልቻለም በምትኩ የሌላ ድምፅ በጆሮው ውስጥ አስተጋባ "
ብር አምባር ሰበረልዎ !
ብር አምባር ሰበረልዎ !
ሸጋው ልጅዎ ! ”

የእስክንድር እና የሳምሶን ድምፅ መሰለው ፡ ጆሮው የሰማ የመሰለውን በዐይኑ ለማረጋገጥ ዐይኑን ገለጠ አሁንም ምንም ነገር የለም ። ዐይኑን እየጨፈነና እየገለጠ ከቅዠቱ ጋር በመጫወት ላይ እንዳለ እንቅልፍ አሸለበው ።

የክፍሉ በር ሲበረድ ከእንቅልፉ ባነነ ብርቅነሽ ነበረች የደም ሰንበር በተጋደመባቸው ዐይኖቹ ውስጥ
ግዙፍ ሆና ታየችው ። ንቅሳቷ ባለበት የሚርገበገብ መሰለው።

"አልተኛህም እንዴ ? ”
"እ ? ”
“ አልተኛህም ወይ ? ”
ገና ከመግባቷ ተወርውራ አጠገቡ ቁጭ አለች « ዘለለና አቀፋት ። ቶሎ ልብሱን አወለቀ፡ ጭኑና ጭኗ ስለ ተጠጋ
ክፉኛ ሞቀው ።

“ አንዴ ቀና በል ፤ የኔ ሸጋ ”

“ እ ? ”

“ አንዴ ቀና በልልኝና በሩን ቆልፌ ልብሳችንን እናውልቅ
ቁና ቁና እየተነፈሰ ቀና አለ " የሴት ልጅ ገላ ለመጀመሪያ ጊዜ በመጠጋቱ በወሲብ ስሜት የልቡ ትርታ ክፉኛ
ይነጥርበት ጀመር ።......

💥ይቀጥላል💥
👍1
#አሃ . . .!

በመጸው ሰማይ ሥር
በቀለም ሸብርቃ
ካ'ዋፋቱም ልቃ
የመስቀል ወፍ ታየች ፤
ወረኃ መስከረም
ለምልማና ደምቃ
ከምድር ማሕፀን
ዐደይ በቅላ ፈካች።

አካል ላባዎቿ .
ከጥዑም ድምጿ ጋር
ከደመናው በላይ
በሰማዩ በራ ፤
ሕብር ፣ ሕብረ ቀለም . .
ከአድማስ ጥግ ላይ
ውብ ቀስተ ደመና
በቃል ኪዳን ሠራ።
ማራኪ ገጽታ ፣
ጤዛ ጠብታዎች
አበባ አካሏ ላይ
እንዳሸበረቁ ፤
ቢራቢሮ ፣ ንቦች
ነፍሳቶች በሙሉ
ከዐደይ ላይ ቀስመው
ሕይወትን ሰረቁ።

ግና . . .
የመስቀል ወፍ ውበት ፣ ድምጿ ቢስረቀረቅ
ዐደይ አበባዋም ፣ ምድሩ ላይ ብትደምቅ
በምን ጥበብሽ ነው . . . ?
ያ'ነኚኽን ውበት፣ ጸጋሽ የሚደብቅ።

ምን ዐይነት ኃይል ነው?
መስህብ ጸጋሽ ኹሉ ፣
አንዳች ምስጢር አለው።

አሃ. . .!
ለካ . . !
ይህ ኹሉ የታየው
አንቺ ስላለሽ ነው።

እኔን የገረመኝ . . .!
ዐደይም ስትረግፍ ፣
የመስቀል ወፍ ስታልፍ
ከመጸው ጋር ዕብራ ፤
ፀሓይም ስትጠልቅ ፣
ጨረቃም ስትጎድል
ዝናቡም ሲያባራ ፤
ጊዜ በቀመሩ
ኹሉን አፈራርቆ
በኃይሉ ሲመራ ፤
ምን ምስጢር ኖሮት ነው . . .?
የቁንጅናሽ ጮራ
በዘላለም ስፍር
ኹሌም የሚበራ።
አሃ . . .!
ለካ . . .!
እንኳንና ኅዋው
ውበትም ራሱ
ካ'ንቺ ነው 'ሚሠራ።

🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#ሚሊዮን ፀሐዮች ሚሊዮን ጨለሞች


ጨረቃ ብቅ አለች ፀሐይ ስትከስም
ያው እንደ ወትሮ ነው
የምሽት የንጋት ፈረቃው አይፈርስም!

የኔ ግን ይለያል
ልቦናየ ቢማስ
ሚሊዮን ፀሐዮች ሚሊዮን ጨለሞች!
ሺ ሰማይ ሺህ አድማስ
ተገልጦ ይታያል።

ስንቴ በጽልመቴ ዙርያየን አዳፈንሁ
ስንቴ በጨረሬ የምድርን ዐይን ወጋሁ
ባንድ ቀን ውስጥ ብቻ
ስንት ጊዜ መሽቼ ስንት ጊዜ ነጋሁ!

በዕውቀቱ ስዩም
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ


#ድርሰት_በትክክል_ገና


....መያዣ መጨበጫ በሌለው ቋጥኝ ላይ ተንጠልጥያለሁ፡፡ የሙጥኝ ብዬ የተጣበቅሁት ድንጋይ ቅቤ እንደተቀባ አሎሎ እያሙለጨለጨ ያሰቃየኛል፡፡ ነፍስና ስጋዬ በጭንቀት ተወጥረው
ይሟገታሉ። ቀና ብዬ ተመለከትኩ፡፡ ወደ ተራራው አናት ለመውጣት የማደርገው ጉዞ ሊደረስበት ይቅርና፤ ከቶም የማይታሰብ ሆኖ አገኘሁት..እንደ ብረት ምጣድ ክብ ሆኖ፤ በአናቴ ላይ ሊወድቅ የተዘጋጀ የሚመስል፤ ግዙፍ አለታማ ድንጋይ አየሁ፡፡ የመሹለኪያ አማራጩን
በፍርሃት ተውጬ አማተርኩ፡፡ አሞራ አይደለሁ በክንፌ አልበር ነገር
ሰው መሆኔን የጠላሁት የዚያን ጊዜ ነው፡፡

ከዚህ በላይ ሽቅብ የመውጣቱ ጉዳይ ተስፋ አስቆራጭ ሆነብኝ::በመጣሁበት መንገድ ለመመለስ ፈለግሁ፡፡ ያለኝ የመጨረሻው አማራጭ እሱ ብቻ ነበር፡፡ ምን ያደርጋል? በወጣሁበት መንገድ የመውረድ ምኞቴም እንደ በረዶ በውስጤ የቀዘቀዘው ጎንበስ ብዬ ቁልቁል ስለመከት ነው፡፡ እንዴት አድርጌ፤ እንደምንስ ብርታቱንና ኃይሉን አግኝቼ፤ የዚያን ያህል ሽቅብ ልወጣ እንደቻልኩ ሳስበው፤ ለራሴ ደነቀኝ፡፡
ማርታዬ፤ የኔዋ ውብ ማርታ፤ ዐይኖቿ እንደንጋት ኮከብ የሚያበሩት ማርታ፤ ከበረዶ የሚነፃፀሩ ውብ ነጫጭ ጥርሶቿ ልብን የሚፈለቅቁት የኔዋ ቆንጆ ፤ በእኒያ አለንጋ መሳይ ጣቶቿ ስትደባብሰኝ
ቀለበቷን ለመሆን የሚያስመኘኝ ፍቅርኛዬ ነበረች፤ ኃይሉን በውስጤ የፈጠረችው::

እነዚያ ውብ ከናፍሮቿ የግማሽ ጨረቃን ቅርጽ ይዘው ፈገግ ስትል፤ ልቤ ያለመወርወርያ ገርበብ እንዳለ መዝጊያ፧ ብርግድ የሚልላት ማርታዬ ነበረች ኃይሉንና ብርታቱን ሰጥታ እዚያ ቋጥኝ ላይ በቅዠት ያስወጣችኝ፡፡ የዛሬው አዳሬን አያድርግብኝና፤ ለወትሮው መንፈሴን በሚያስደስት በልዩ ምናባዊ ዓለም ውስጥ የሚያስዋኘኝ ጣፋጭ መዓዛዋ አሁንም ድረስ ያውደኛል፡፡ እያንዳንዳቸው ጥቃቅን ህዋሳቶቼ ከፍቅር
ድርና ማግ እንደተሰሩ ሁሉ፤ መላ አካላዊ ተፈጥሮዬም ወደር የማይገኝለት የማርታዬ የፍቅር ጥልፍና የሽመና ጥበብ ውጤት ሆኖ ይሰማኛል። ጣፋጭ አንደበቷ፣ ዜማዋ፣ ለዛዋ ...ቃናዋ ... ዛሬም ህያው
ነው ለኔ፡፡

ፍቅር የህይወት ቅመም መሆኑን ከማንም ባላነሰ የተረዳሁ ይመስለኛል፡፡ በእነዚያ
ባልታደልኩባቸው ጊዜያቶች ውስጥ
የህይወትን ለዛ ቢስ ጣዕም እስከሚበቃኝ ድረስ አጣጥሜዋለሁ። የህይወቴ ቅመም በድንገት ስትለየኝ ህይወቴ ባዶ ሆነች፡፡ አዎን ጭውው... ያለ መጋዘን በውስጡ ወደል ወደል አይጦች የሚሯሯጡበት
መጋዘን... በኔም ባዶ ህይወት ውስጥ ጭንቀትና ብስጭት እንደልባቸው ይሯሯጡበታል እሷን ባስታወስኩኝ ቁጥር አካሌ እሳት ውስጥ እንደወደቀ ሙዳ ሥጋ ጭብጥ ኩርምት እርር ድብን ይላል፡፡

ፍቅር የራስ መውደድ ነፀብራቅ ነው የሚሉ ካሉ ተሳስተዋል፡፡እኔ እሷን የማያት ከራሴ አስበልጬ ነው። እራሴንም በሷ ውስጥ አልወደድኩም፡፡ እንደዚህ ዓይነቶቹ በፍቅር አበድን! አንቺ ከሌለሽ፤ አንተ ከሌለህ ፤ እየተባባሉ ሲሸነጋገሉ ከቆዩ በኋላ፤ እንደኛው በአጋጣሚ ከተለየ
በማግስቱ ሁሉንም ነገር እንዳልነበረ ረስተውት፤ ከአዲስ ፍቅረኛ ጋር አዲስ ዓለም ለሚቀጩት ወረተኞች ሊሆን ይችላል ፡፡ በገቡት ቃል ኪዳን ፀንተው፤ በመንፈስ አብረው ቆይተው፤ እስከ ወዲያኛው የአካል ግብአተ መሬት ድረስ ፍቅረኞቻቸውን የሚከተሉ መኖራቸውን አልዘነጋውም።
ማርታዬ ለኔ በውስጤ በቅላ፤ አድጋና ጎምርታ ለፍሬ የበቃች የህይወቴ መሠረት ነች:: ፍቅራችን በድቡሽት ላይ የተገነባ ቤት ዓይነት አልነበረም፡፡ ሲቀር የሚቀርም አይደለም፡፡ በልቤ ውስጥ ተተክላ ሥሮቿን ከራስ ጠጉሬ እስከ እግር ጥፍሬ ዘርግታ አድጋና አብባ የምትገኘው
ማርታ ፍቅሬን በቀላሉ ከልቤ ውስጥ ነቅዬ ልጥላት አልቻልኩም።
ከእንግዲህ በኋላ ማርታን ከኔ ልብ ውስጥ ነቅሎ ከማውጣት ይልቅ ነፍሴን ከህያው አካሌ ውስጥ ነቅሎ ማስወጣቱ ይቀላል። ማርታ ከአቅሜ በላይ በቤተሰብ ተፅዕኖ ዐይኖቿ እንደ ጅረት ውሃ ያለማቋረጥ እምባቸውን እየረጩ ብትለየኝም በሷ አልፈረድኩባትም።
እሷ እኮ ለኔ ልዩ ሰው ነበረች፡፡ ልዩ የምትሆንባቸው ብዙ ምክንያቶች አሉኝ፡፡ ከህይወት ታሪኬ አጀማመርና ሂደት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው:: የማርትዬ እንባ አሁን ድረስ ሲፈስ ይታየኛል፡፡ ከዚያም
በኋላ ሰው አትሆንም። በሀዘን የቆሰለው ልቧ በቀላሉ የሚድን አይሆንም፡፡ ህመሟ ጠልቆ ይጠዘጥዘኛል፡፡ እንባዋ እንደ እንፋሎት ያቃጥለኛል፡፡ ለምን ትሉኝ ይሆናል፡፡
“ይዘኸኝ ጥፋ ሲራኬ እንሂድ... እንሽሽ” እያለች ፍርሀቷን ስትገልጽልኝ ችላ እያልኳት፤ እንደፈራችው ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተለያይተን
በመቅረታችን ነው፡፡በደለኛነት ማቆሚያ ወደሌለው የአድማስ ጫፍ ያስሮጠኛል።
እንደጉም ወደማይጨበጥ ዓለም ይወሰደኛል። ወደማልደርስበት አዲስ
ዓለም... እሮጣለሁ፡፡ ፀፀት አእምሮዬን ይገዘግዘዋል። ከእንባ ጭጋግ ባሻገር እጆች ይውለበለቡልኛል፡፡ ነጫጭ ጥርሶች እንደተገሸለጠ የመስኖ በቆሎ እሸት ተውበው ልቤን ያማልሉታል። የብር ጉልላት የመሰሉ ዓይኖች እየተንከባለሉ ሆዴን ያባቡታል። ልደርስባቸው እሮጣለሁ::በጣም እሮጣለሁ፡፡ መቆሚያ የሌለው መድረሻ የሌለው ...የማይጨበጥ ከንቱ ሩጫ....

በድን አይደለሁ ትኩስ ደም በውስጤ ይዘዋወራል። ከአጥንትና ከጅማት የተዋቀረው አካሌ ለኔነቴ መገለጫ ብቸኛው ህያው ምስክር ቢሆንም ውስጤ ግን በህልም ዓለም የሚመራ ዓይነት ሆኗል። አስባለሁ፣አሸታለሁ፣ አዳምጣለሁ፣ እቀምሳለሁ፣ በስሜት ህዋሳቶቼ የማሸታት ቆንጂዬዋን ውብ ጠረን ያላት ማርታዬን ነው፡፡ የዚህችን
ማለቂያና ማብቂያ፤ የሌላት ብልጭልጭ ዓለም ቅጭልጭልታና ጩኸት የማዳመጫ ጆሮ የለኝም፡፡ ለጆሮ ሳይሆን ለልብ የሚሰማ ጣፋጭ ድምጽ
በውስጤ ያንሾካሹካል ::
ሰመመን ወስዶ ዳር በሌለው ሰፊና ውብ ዓለም ውስጥ ያዝናናኛል፡፡ ከሳሽና ተከሳሽ በዳይና ተበዳይ፣ አባራሪና ተባራሪ፣ አጥፊና ጠፊ፣ ወደሌለበት ወደ አንድ ልዩ ዓለም... አዳምጣለሁ፡፡ ኮሽታ አይሰማም፡፡ ህይወት ፀጥ እረጭ ብላለች፡፡ ሁሉም በሰላም የራሱን
ህይወት ይመራል፡፡ በአዲሱ ዓለም፡፡ ያለረብሻ፣ ያለስቃይ፣ ያለረሀብ ያለሀዘን፣ ያለከሳሽ ተከሳሽ፣ ያለተቃራኒ በአንድ አቅጣጫ ብቻ ... ነጣቂና ተነጣቂ በሌለበት በአዲሱ ዓለም... ድህነት ሀብታምነት በሌለበት ውብ ዓለም ህይወት ትጓዛለች፡፡
ዐይኖቼ ፈጠዋል ቁምነገሩ ዐይን ከሆነ እኔም ማለፊያ ትላልቅ ዐይኖች ነበሩኝ፡፡ ከሰው ልጅ ውጫዊ ባህሪ በስተጀርባ የአውሬነት ፀባዩን ማየት የማይችሉ ዐይኖች። በጥርጣሬ ያልተሞሉ ፈዛዛ ዐይኖች፡፡ እንደ ነብር ዐይኖች እየተንቀዠቀዡ አካባቢያቸውን በጥርጣሬ የማይቃኙ ዐይኖች፡፡
ሻምበል ብሩክ መጽሐፉን ከደነና አርዕስቱን ተመለከተው፡፡ እንደገና ጀርባውን ገልብጦ የደራሲውን ፎቶግራፍ በጥንቃቄ አየው።እንደገናም የራሱን ህይወት በመጽሀፉ ታሪክ ውስጥ አየው። በዕድሏን በማርታ፤ ውስጥ ሲራክን ደግሞ ዐራሱ ውስጥ፡፡ የራሱ የህይወት ታሪክ ቅንጭብጭብታ በድርሰቱ ውስጥ ተጠቃቅሶ ስላገኘው ያለዕረፍት አንብቦ ለመጨረስ ጉጉት አደረበት። የማርታ መጨረሻዋ ናፈቀው፡፡ የባለታሪኩ የሲራክ የህይወት አቅጣጫ ወዴት እንደሚያመራ ለማወቅ ልቡ ተንጠለጠለች...
ዐይኖቹ እንባ እንደቋጠሩ በዕድሏን አሰባት፡፡ የልጅነት ፍቅራቸው ታወሰው፡፡ የአደፍርስ ምስል ከፊቱ ድቅን አለ። ፍቅሩን የነጠቀው ነጣቂ፡፡በዚህም ምክንያት ለረጅም ጊዜ ስሜቱ ቆስሏል፡፡ ልቡ ደምቷል። ፍቅርን ሸሽቷት ኖሯል፡፡ ፍቅር ግን እሱ ሲሸሻትም እሷ አልሽሸችውም። ይኸውም እንደ አዲስ መንፈሱን የሚንጥ፤ የተቀበረ ስሜቱን
👍3
የተቀሰቀሰበት፤ የፍቅር ጥንስስ፤ በድሏን በምትመስል ቆንጆ ልጅ በትህትና ድንበሩ ውስጥ ቀስ በቀስ ልቡን እየሸረሸረው ነው...አሁን እንደባለ ታሪኩ ሲራክ እራሱን አይኮንንም፡፡ ዕረፍት አጥቶ ሰሀሳብ የባከነበት የመከራ ጊዜ ማክተም አለበት፡፡ ያንን አላነብም ብሎ ትራስ አድርጉት የቆየውን አስደናቂ መጽሀፍ እንቅልፉን አጥቶ እስከ እኩለ ለሊት ድረስ አነበበ ስለንባብ የነበረው አመለካከት ተቀየረ፡፡በአንባቢ የሚታወቀውና የአራተኛ አመት የማኔጅመንት ተማሪ የሆነው ጓደኛው አቤል የተናገረውን አስታወሰ ፡፡ ፊደል ከቆጠረ በኋላ መጽሃፍ የማያነብ ሰው አረምና ሙጃ አብቅሎ ከሚንቀሳቀስ እዳሪ መሬት ተለይቶ አይታይም። ጥበብ የህይወት ማእድ ነች፡፡ የቀይ ወጥና
የአልጫ ብፌ ጠግቦ በቁንጣን ከመታመም ይልቅ የጥበብን ማእድ በገፍ
ለነፍሱ የሚጋብዝ ብልህ ነው፡፡ ሰእል፤ ስነጽሁፍ፤ ትያትር፤ ሲኒማ፤
ሙዚቃ የጥበብ ማእድ ብፌዎች ናቸው፡፡ ከጥበብ ማእድ ደጋግሞ የሚመገብ እያደር ይራባል እንጂ በቁንጣን አይታመምም :: በተለይ ስነጽሁፍን ለማድነቅ የተፈጥሮ አይንና ጆሮ ብቻ ሳይሆኑ ቢያንስ ፊደል መቁጠርን የሚጠይቅ ፤በስክሪንና በመድረክ ስፋት ልክ ሳይሆን በጭንቅላትህ አድማስ ልክ አለምን የምትቃኝበት መድረክ በመሆኑ
ስነጽሁፍን ልታፈቅር ይገባል ” ይለው ነበር ሁል ጊዜ፡፡
“እውነቱን ነው!!” አለ፡፡ ከመጽሃፍት ራሱን ያገለለባቸውን ጊዚያት በጸጸት አስታወሰና መጽህፉን ከከደነ በኋላ....
“አንተ ታውቃለህ አምላኬ” ብሎ ብርድ ልብሱ ውስጥ ገብቶ ተጠቀለለ...

በእቴጌ ጣይቱ ስም የተሰየመው ሆቴል በአዲስ አበባ ውስጥ ከሚገኙት አንጋፋና ነባር ሆቴሎች መካከል አንዱ ነው። ጥንት አራዳ አሁን ደግሞ ፒያሳ ተብሎ በሚጠራው የከተማዋ እምብርት ላይ የሚገኝ ትልቅ ሆቴል....
ሻምበል ብሩክና ትህትና የተቀጣጠሩት በዚሁ ሆቴል ሲሆን ከሆቴሉ ግቢ ተርፎ አውቶሞቢሎች ደጁን አጥለቅልቀውት ይታያል።
ሻምበል ብሩክ ከቀጠሮው አምስት ደቂቃ ቀደም ብሎ በመምጣት እየተጠባበቃት ነው የትናንትናው ቀጠሮ የተለዋወጡበት ምሽት በምጥ ነግቶ፤ ቀሪውን አሥራ ሁለት ስዓት ደግም በሥራ ቦታቸው ላይ
ስላሳለፉት በአካል እስከሚናኙ ድረስ ተነፋፍቀው ነበርና፤ በርቀት ተያይተው ተሳሳቁ፡፡.......

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍3
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ስምንት


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

....በማግሥቱ ጠዋት ከቀጠሮው ሰዓት ቀድሞ ጆሊ ባር የተገኘው እስክንድር ነበር። ያደረበት ቤት ስላልተስማማው
በሌሊት ነበር ሾልኮ የወጣው ። የቤቱ አለ መስማማት ብቻ ሳይሆን የሰው ዐይን ፍራቻም ነው “ አላሁ አክብር” ሳይል ያስወጣው ። የገዛ ኅሊናው ዐይን ሲያለቅስ እንባውን አድርቆ ሲልከሰከስ እያደረ ' የሌሎችን ዐይን ለምን እንደ
ሚፈራ ሁሌም ይገርመዋል ። ባደረበት ቤት አንግቶ፡ ተዝናንቶ ቆይቶ አያውቅም ።

ይህን ልምድ ከየት ይሆን የቀዳነው ? ” ሲል አሰበ በዩኒቨርስቲው ውስጥ በትምህርት ወራት ቀለም ላይ ተደፍቶ
መክረም ፡ በዕረፍት ሳምንታት ደግሞ ኪስ እስከ ተቻለ ድረስ በአልኮል ማበድና በየበረንዳው ማደር ፈሊጥ እየሆነ መምጣቱ ነበር ያሳሰበው ። በዛሬው ዕለት እንኳ እንደ እሱው የሰው ዐይን እየፈሩ ከያደሩበት በረንዳ በሌሊት እየተሾለኩ " ጸጉራቸው እንደ ተንጨፈረረ ወደ ካምፓስ ቢሮ ያያቸው ተማሪዎች ቁጥር ትንሽ አልነበረም ።

ሁኔታው በትምህርት ተጨንቆ የከረመን አዕምሮ የማዝናናት አዝማሚያ ይመስላል” ሲል ሐሳቡን ቀጠለ
“ ታዲያ ከሰው ዐይንም ; ከዛ ኅሊናም የማይሸሹበት ሌላ መዝናኛ መፍጠር አይቻልም ወይ ? ተማሪው ከተባበረ ከፈተና በኋላ ባለው የዕረፍት ጊዜ ውስጥ እንደየዓቅሙ ገንዘብ አዋጥቶ ' የሙዚቃና ሌሎች የተለያዩ ትርኢቶችን እንዲሁም አዝናኝና አነቃቂ ውድድሮችን ማዘጋጀት፥ በቡድን ሆኖ ከከተማ ወጣ እያሉ ብርቅና ድንቅ ቦታዎችን መጐብኘትና የመሳሰሉት ልምዶች ቢዳብሩ ጤናማ መዝናኛ ይሆኑ
ነበር ። ታዲያ ይህን በጐ ተግባር ለማስተባበር የግንባሩን ቦታ ማን ይውሰድ ? ?

በራሱ ሣቀና ሲጋራ ለመፈለግ ኪሱን ይደባብስ ጀምር ትላንት ማታ ሌላ፡ ዛሬ ጠዋት ሌላ መሆኑ ነው ያሣቀውም
የአንድ ሰው ሁለት ልክ ? አለ በልቡ።

ሣቁ ከፊቱ ላይ ሳይጠፋ ሳምሶን ጉልቤው ደረሰ። ፊቱን ጭፍግግ አድርጐታል • እሱነቱ አስጠልቶት ራሱን የሚጥልበት ቦታ ያጣ ሰው ይመስላል "

“ ታድያስ ? ” አለው እስክንድር ፈገግ እያል ።

ሳምሶን አፉ መናገር እንዳቃተው ሁሉ “ መቼም አልሞትኩም ! ” በማለት ዐይነት አፍንጫውን አጣሞ አንገቱን ወደ ግራ አዘነበለ እጆቹን ኪሶቹ ውስጥ እንደ
ከተተ ሊቀመጥ ሲል ሱሪው የመተርተር ድምፅ አሰማ።

“ እናትክን ! ” አለው ሱሪውን ።

ጥርሳም እንዳትለው ሱሪው ጥርስ የለው አለና እስክንድር ቀለደበት ።

ሳምሶን ፈገግም አላለም "ቢኮረኩሩትም የሚሥቅ አይመስልም

“ ምነው ደበረህ ?” አለው እስክንድር ሣቁን እየዋጠ ።
“ ምን እባክህ ነጭ ናጫ ሴት ነች የገጠመችኝ፡እንዲሁ ስንበጣበጥ ነው ያደርነው "

አይዞህ አንድ ነን ። እኔም ቀዝቃዛ አሮጌት ይዤ ነው ያደርኩት መጠጥ ምን የማይሠራው አለ? ብቻ አትፍረድባቸው ። የእንጀራ ጉዳይ ሆኖባቸው ነው እንጂ ሰልችቶቸዋል "

“ ጥርሳሞች ! ” አላቸው ሳምሶን በልቡ ። ከእስክንድር ጋር መከራከርም መጫወትም አልፈለገም ። መላ ሰውነቱ
ደክሞአል " ለመፍታታት ያህል እንኳ የጠዋት ስፖርት አልሠራም። ሕይወትን የመሰላቸት ስሜት ተሰማው ፡ ፊቱን
በመስታወት ባያየውም በስሜቱ ጠውልጎ ታየው ። የጠጣበትን ቡና ቤት ያጠጣውን ገንዘብና አብሯት ያደረችውን ሴት በልቡ እየረገመ ጠረጴዛውን በቡጢ ደበደበ "

“አቤት!ምን ልታዘዝ?” ሲልአሳላፊው ከተፍ አለ ።
"አንድ ጠርውስ ቀዝቃዛ አምቦ ውሃ ”
“ አዎ ጎሽ ፡ የተቃጠለ አንጀት ለማራስ” አለ እስክንድር ተደርቦ ።

አምቦ ውሃው ቀርቦላቸው እየጠጡ በመጫወት ላይ ሳሉ አቤልን በውጭው መስተዋት በኩል አዩት። ከኋላው
የሚያባርሩትን ያህል በፍጥነት ነበር ወደ እነሱ የሚገሰግሰው ። የእስክንድርና የሳምሶን የተደበረ ስሜት አቤልን
ሲያዩ ተነቃቃ ። ወሬውን ለመስማት አጠገባቸው እስኪደርስ ተቻኮሉ። እሱም ከውጭ ሲያያቸው ዐይናቸውን አፍሮ
በሆዱ አቀርቅሮ ነበር የተጠጋቸው» ማታ በቅዠት መልክ የሰማውን “ ብር አምባር ሰበረልዎ ” አሁን ለቱ ሰበውን የሚሉት መሰስው ።

“ እህሳ ? ሌሊቱ እንዴት ነበር ? ” አለው ሳምሶን' ቀድሞ ሊጨብጠው እጁን እየዘረጋ።

ጥሩ ነበር” አለ አቤል ሁለቱንም ከጨበጣቸው በኋላ ጠርሙሱ ውስጥ የተረፈውን አምቦ ውሃ በብርጭቆ
እየቀዳ ። ጠጥቶ እንደ ጨረሰ በእርካታ ተንፍሶ፡ “እንሒድ እባካችሁ ” አላቸው ።

"ቁጭ በልና ተጫወት እንጂ ” አለው ሳምሶን ለወሬው ጓጉቶ ። አቤል ግን መቀመጥ አልፈለገም ። ወደ ካምፓስ ለመሔድ ቸኩሎአል ። በዩኒቨርስቲም ግቢ ውስጥ አንዳች ነገር ጥሎ ያደረ ይመስል ልቡ ተሰቅሎአል ። እስክንድርም ይህን ስሜቱን ስለ ተረዳለት ለመሔድ ተነሣ።

ወደ ስድስት ኪሎ ሲጓዙም ሳምሶን ከእቤል የመስማት “ጥማቱ እንደ ቀጠለ ነበር ። በዝምታ ትንሽ እንደ ተራመዱ "

“ ታዲያስ ፡ እንዴት ነበር ? ” ሲል ይጠይቀዋል የሴት ተግባሩን አስጐልጉሎ ለማናዘዝ በሚጥር ጥልቅ ስሜት ።

“ ደኅና ነበር ይላል አቤል ነገሩን ቸል ብሎ ለማሳጠር በሚጥር ስሜት ። ሳምሶን በዚህ መልስ አይረካም

"ብርቅነሽ እንዴት ነች ? ” ሲል ደግሞ ሊያወጣጣ ይሞክራል ።

“ ብርቅነሽ ጥሩ ሴት ነች” ሲል አቤል ነገሩን በአጭሩ ይደመድመዋል ።

አቤል ከብርቅነሽ ጋር ምን ዐይነት የመጀመሪያ ሌሊት እንዳሳለፈ ለመስማት ሳምሶን ብቻ ሳይሆን እስክንድርም
ጓጉቶ ነበር ። የብርቅነሽ ጥሬነት ፡ ግልጽነትና ጣፋጭነት ሳያስቡት በሁሉም ልብ ውስጥ ግልጽ ያልሆነ የፍቅር
ስሜት አሳድሮባቸው ነበር። ያም ሆነ ይህ፡ አቤል እንደ ጠበቁት በሰፊው የሚያወራላቸው አልሆነም ። ጓደኛሞች እንዲህ ዐይነት ሌሊት አሳልፈው ጠዋት ሲገናኙ ስለ አዳራቸው ሁኔታ ወይም አብረዋት ስላደሩት ሴት ማውራት
የተለመደ ቢሆንም ፥ ለአቤል እንግዳ ነገር ነበር ። ስለ አዳሩ እንዳይናዘዝ የፍረትና የቁጥብነት ስሜት ኅሊናውን
ጨምድዶ ያዘው ።

ብርቅነሽ የትዕግሥትን ቦታ ባትወስድም በአቤል ልብ ውስጥ የተወሰነ ዳርቻ ይዛ ነው ያደረችው ። ለወሲብ የመጀመሪያ ሴቱ በመሆንዋ ብቻም አይደለም ። እስዋም ራስዋ ሁኔታውን በማየትና ሳምሶን የነገራትን በማገናዘብ
ለአቤል ቀና ስሜት ስለ ነበራት በባነነ ቁጥር አብራው ስትባንን ነው ያደረችው ። የልቧን አጫውታው የልቡን ምስጢር ወስዳለች ። ግልጽነቷና ፍቅራዊ መስተንግዶዋ አስገድዶት አቤልም ስለ ትዕግሥት ሲያጫውታት ነው ያደረው።
የትዕግሥትን ጉዳይ ለብርቅነሽ ግልጽ ማውጣቴ የቆረቆረው ጠዋት ከተለያት በኋላ ነው ። በግትርነት ተወጥሮ የነበረው መንፈሱ እየላላ መምጣቱ ለራሱም ተሰማው ። ምስጥሬ ብሎ ደብቆ የያዘውን የትዕግሥትን ነገር በመጀመሪያ ለሐኪሙ ፡ በትላንቱ ምሽት በመጠጥ ኃይል ለእስክንድር ሌሊቱን ደግሞ ለብርቅነሽ መናዘዙን ሲያስታውስ የመንፈሱ መላላት ታወቀው ።

ሳምሶንም ሆነ እስክንድር የጓጉትን ያህል ሳያወራቸው ከዩኒቨርስቲው በር ደረሱ ። ግቢው ጭር ብሎአል ።ለወትሮው ቢሆን ይህ ሰዓት ወደ ትምህርት ክፍል መግቢያ ጊዜ በመሆኑ መራወጥ ይታይበት ነበር።ዛሬ ግን ገና ከእንቅልፉ ያልተነሣም ኘለ ። የሚነቃነቅ ተማሪ አይታይም ።

እነ አቤል ግቢ ውስጥ ከገቡ በኋላ፥ወደ መኝታ ቤታቹኑ የሚወስደውን ጠምዛዛ መንገድ ሲይዙ አራት ልጃገረዶች
ከሩቅ ተመለከቱ ። ልጃገረዶቹ ሻንጣ ሻንጣቸውን ይዘው ከግቢው በመውጣት ላይ ነበሩ ። ሦስቱ፡ ልጃገረዶች እነማን
እንደሆኑ ሦስቱም ወንዶች ከመቅጽበት ለዩኣቸው ትዕግሥት፡ ማርታና ቤተልሔም ነበሩ ። ሁሉም ያላወቋት አንዷ ልጃገረድ የቤቴልሔም የመኝታ ክፍል ጓደኛ ነበረች
አቤል ደነገጠ
👍1
በአንዴ ገጽታው ተለዋወጠ ። ሻንጣ ይዘው ወዴት ነው ? ማርታና ቤተልሄምስ ይሒዱ ግልግል
ነው ። ትዕግሥት ግን እኔን ጥላ ወዴት ነው የምትሔደው? ወደ ቤታ ወደ ደብረ ዘይት ? አይደረግም ? ” ሲል አሰበ ።
ልቡ የድንጋጤ ታምቡር ይመታ ጀመር ።

እስክንድር የአቤልን ሁኔታ ለማጤን ጊዜ አልወሰደበትም ። እነሱን ከነሻንጣቸው ሲያይ፥ ፈጥኖ የአበልን ገጽታ ነው የተመለከተወ ምን ስሜት ሊሰማው እንደሚችል ጠንቅቆ ያውቃል ። ከልጃገረዶቹ ጋር ፊት ለፊት ያገጣጠማቸውን አጋጣሚ በልቡ ረገመ ትንሽ ብንቆይ ወይም ትንሽ ብንቀድም ኖሮ፥ መንገደ ላይ አንገናኝም ነበር የሚል
ከንቱ ጸጸት ተሰማው ።የአገጣጣሚውን መጥፎ ጎን እምብዛም ያላጤነው ሳምሶን ከልጃገረዶቹ አጠገብ ሲደርሱ ነዉ ነጻ
በሆነ ስሜት • “ ታዲያስ? በጠዋት ወዴት ነው? ” አላቸው። ቤተልሔምን ብሎ ነው እንጂ ከትዕግሥትና ማርታ ጋር ንግግር የለውም ፡

“ እናንተስ በጠዋት ከየት ነው ? ” አለች ቤተልሄም ሁሉንም በተራ እየጨበጠች ።

ማርታ ምላሷ አምልጧት በረንዳ አድረው ይሆናል ! ” ልትል አስባ ለትንሽ መለሰችው። አቤል መሐላቸው ማየቷ ነው ያሳፈራት ። ከእነሱ ጋር ደርባ ልትተቸው አልደፈረችም ።

ለተጠየቁት ጥያቄ ከሁለቱም ወገን መልስ የሰጠ የለም ። ነገሩን አደባብሰው የመጨባበጡን ሥነ-ሥርዓት
ያካሒዱ ጀመር። የእስክንድርና የአቤል ሰላምታ አለዋወጥ ዘዴ የተሞላበት ነበር።እስክንድር በመጀመሪያ ቤተልሔምንና ትዕግሥትን ጨብጦ ማርታን መጨረሻ ያደረገበት ምክንያት አለው ከጨበጣት በኋላ እጁን እጅዋ ውስጥ ለማቆየት ፈልጎ ነው ። አቤልም ለተመሳሳይ ምክንያት ትዕግሥትን መጨረሻ ጨበጣት ። ነገር ግን እንኳንስ እጅዋን ይዞ ሊቆይ ቀርቶ አንድ አፍታ ዘርግቶ ለመመልሱም ተንቀጥቅጦ
ነበር ። ቀና ብሎ ፊቷን ሳያይ ፈንጠር ብሎ ቆመ እዚህ አካባቢ ትዕግሥትን በተመሳሳይ ሁኔታ ሲያገኛት ሁለተኛ
ጊዜው መሆኑ ነው። አንዴም እንዲሁ ማርታና ቤተልሔም ይዘዋት ወደ ሠርግ ሲሔዱ አጋጥመውት የረገማቸው እዚሁ
መውጫ ላይ ነበር ። እና የሁኔታዎች መደጋገም አስደነቀው። እንደ ተቀጣጠረ ሰው መውጪያና መግቢያ ላይ መገናኘቱ
አስገረመው " የ እውነትም የፍቅር አምላክ ይኖር ይሆን እንዴ ?” ሲል አሰበ “ ወይንስ ደግሞ ሳይኮሎጂስቶች ቴሌፓዚ. ” እና “ ክሪቮያንስ ” የሚሉት የርቀት ግንኙነት በእርግጥ ለፍቅረኞች ሥሠራ ይሆን ? ”

ይህን ጠልቆ ለማሰብ ጊዜ አላገኘም ። አሁን እንገብጋቢው ጥያቄ የትዕግሥት መሔድ ነው የ አስር ወይም አሥራ አምስት ቀን ተለይታው ልትከርም ? እንዴት ይሆናል ? ያን ሁሉ ቀን ዐይኑ ምን እየተመገበ ይኖራል ?

ቀስ ብሎ አንገቱን አዙሮ ሰርቆ ተመለከታት ። አጠገቧ እንዳይቆም የተከለከለ ይመስል ከጨበጣት በኋላ ፈንጠር ብሎ ለሁሉም ጀርባውን ሰጥቶአችው ነበር የቆሞው ።
አቋቋሙም ሳምሶንና እስክንድር ከሴቶቹሰ ጋር ያወሩ ስለ ነበር እስኪጨርሱ በመጠበቅ ዐይነት ነው ። ሰርቆ ሲያያትና ሰርቃ ስታየው ፥ ድንገት ዐይናቸው ተገጣጠመ። የሁለቱም ልብ ዘለለ። እሱ ቀድሞ አይኑን ሰበረ የሚሆነውን ለማየት ድርቅ ብላ አየችው አስተያየቷ ብሽቀትና የመንፈስ መብከንከን ያዘለ ይመስላል ።

ትዕግሥት ራሷ ፡ ከአቤል ጋር ባላት ድፍን ግንኙነት እየበገነች መምጣት ከጀመረች ሰንብታለች ። ሰውን ለሁኔታዎች ተገዥ የሚያደርገው መላመድ መሆኑን ተገንዝባለች ። የአቤልን የዐይን ፍቅር ብትሽሸውም አልሆንላትም ።እሱ ተደብቆ ሳያያት ማደር እንደማይቻለው ሁሉ ፡
እሷም ሳታየው መዋል እንዳቃታት እየተረዳች መጥታለች።የሚያበግናት የፍቅሩ መልከ ቢስነት ነው ። መተያየትን
ፈልገው ፥ ሲተያዩ መተፋፈር ፤መገናኘትን ፈልገው ፡ ሲገናኙ መኮሰታተር እየተዋደዱ መራራቅ ፤ የዚህ አስጨናቂ ሁኔታ መጨረሻው ምን ሊሆን እንደሚችል ብታወጣው ብታርደው ፥ ብታሰላስለው ልትደርስበት አልቻለችም ።ሁለቱ የያዙት የማይገናኝ ቀጥታ መንገድ መስሎ ታያት

ከዚህ በተጨማሪ የትዕግሥትን ልብ ያቃጠለው የአካባቢው ወሬ ነው ። ባለፈች ባገደመች ቁጥር ከተማሪው
ሹክሹክታ መሐል የአቤል ስም ጆሮዋ ውስጥ ጥልቅ ይላል ገና ፈተና ከማለቁ ምሽቱን በሴቶች መኝታ ቤት ውስጥ
ከሞላ ጎደል ሐሜቱ ያተኩረው በእሷና በአቤል ሁኔታ ላይ ነበር ። ሰምታ እንዳልሰማች ጆሮዋን በመድፈን ኣካባቢውን መጋተር አልቻለችም ። ፈተና ባለቀ ማግሥት ግቢውን ለቅቃ ለመውጣት የተገደደችውም በዚሁ ምክንያት ነው ።ለተወሰኑ ቀናትም ቢሆን ፥ ከአቤል ዐይን መራቁ ለእሷም ከብዷታል ሆኖም ማርታና ቤተልሔም ለዕረፍት ግቢውን ስለሚለቁ ብቸኝነት እንዳያጠቃት ፈርታ ነው አብራቸው ግቢውን ለመልቀቅ የወሰነችው።

ትዕግሥት ምነው ፈዘዝሽ ? ” አላት እስክንድር ከማርታ ጋር የያዘውን ጨዋታ አቋርጦ። ከጨበጣት ጀምሮ እጅዋን ሳይለቅ እያዋራት ነበር ። ሳምሶን ጨዋታ አጥቶ “ ታዲያስ ? ” ብሎ እየጠየቀ ፥ “ "እና ” ተብሎ እየተመለሰለት ፥ለወጉ ያህል አብሯቸው እንደ ቆመ ነበር።

ትዕግሥት እስክንድር ለጠየቃት ጥያቄ መልስ ሳትሰጠው ዝም ብላ ተመለአተችው። አስተያየቷ ጤናማ አልነበረም ። የሦስቱንም ወንዶች የደከመ አካልና የጠወለገ ፊት በማየት ውጭ አድረው መምጣታቸውን ለመገመት ችላለች። ግን ውጭ የት ? እና ምን ሲያደርጉ ? ቅናት ተሰማት ። እስክንድር አቤልን እንዳበለገው አድርጋ በመገመት በጥላቻ አየችው። አቤል በማርታ ላይ ያለውን አይነት መጥፎ ስሜት ትዕግስት በእክንድር ላይ ማሳየት ጀመረች።

እስክንድር ይህን የትዕግሥትን ውስጣዊ ለውጥ ሳያጤን ፥ “ ማርታና ቤተልሔም እንኳ ከካምፓስ ቢወጡም እዚሁ ከተማ ናቸው ፤ አንቺ ግን የት ልትሔጂ ነው ? ”
ብሎ ጠየቃት ።

አቤል የዚህን መልስ ለመስማት ጆሮውን አሰላ ።

ትዕግሥት የእስክንድርን ጥያቄ ለመመለስ ተገደደች ። “ እኔም ወደ ሀገሬ ወደ ደብረ ዘይት ነዋ ! ዕረፍቱን ከወላጆቼ ጋር ላሳልፍ ብዬ ነው ።

የአቤል ልብ እንደገና ተንፈራገጠ ። ወደ ወላጆቿ ዘንድ ለመሔድ መነሣቷን ገና ሻንጣዋን ሲያይ የገመተ ቢሆንም ፡ ከእሷው አፍ መስማቱ የባሰ ልቡን ረበሸው ።ሆዱን አንቦጫቦጨው ። ደብረ ዘይት ከአዲስ አበባ ስንት ኪሎ ሜትር ይሆን ? በስም እንጂ አቤል ቦታውን አያውቀውም ። እና ቆሞ ሲያሰላስል ትዕግሥትን ሳያይ የሚከርመው
ዐሥራ አምስት ቀን ዐሥራ አምስት ዓመት መስሎ ታየው።

“ እንሒድ እባካችሁ ! ” የሚለው የሳምሶን ድምፅ አቤልን ከሐሳቡ እስክንድርንም ከወሬው አቋረጣቸው ።ሆዱን ስለ ሞረሞረው፥ ከሴቶቹ ለመለየት ቸኩሎ ነበር ።

አቤል የሳምሶንን ድምዕ ተከትሎ መራመድ ጀመረ ።ሴቶቹ ለስንብት ዐይናቸውን አቁለጨለጩ ። እስክንድር
ግን የያዘዉን የማርታን እጅ መልቀቅ አልፈለገም ነበር ።

“ እሺ እንግዲህ ! ታዲያ ዕረፍቱን የት ትገኝያለሽ ? ” አላት የግዱን እጅዋን እየለቀቀ ።

“ ደውልልኛ ! ” አለችና ስልክ ቁጥሯን ነገረችው ።ከእሱ ጋር ስታወራ ወደ አቢል እያየች ነበር ። አቤል ሲናገር ወይም ሲጫወት መስማት ትፈልጋለች ። ይህ ጅንን ፥ ኩሩ ሰው ሲተነፍስ ምን እንደሚመስል መስማት ትመኛለች ።
ለምን እንደማያናግራት አይገባትም ። አጠገቧ አንድም ቃል ተንፍሶ አያውቅም ሲጨበጣትም እጁን እየዘገነነው ነው ። ልክ እንደ አባቱ ገዳይ ነው የሚያያት ።

አሁንም ሳይሰናበታቸው ሔደ ። እስክንድርና ሳምሶን ልጃገረዶቹን ተሰነባብተው ሲከተሉት ኮቴአቸውንና ድምፃቸውን ሰማ ። ከትዕግሥት ጋር ጀርባ ተሰጣጥተው ተለያዩ እሷ ወደ ውጭ እሱ ወደ ግቢ ። ዝም ብሎ ወደፊት ለመቀጠል አልቻለም ። ዘወር ብሎ ሊመለከ
👍1
ታቸው ፈለገ ። እስክንድርና ሳምሶን በአድራጐቱ ሲያፌዙበት በሐሳቡ ታየው። አልዞረም ።

መለየት ! ለጥቂት ቀናትም ቢሆን ከሚወዳት ልጅ ዐይን መራራቅ ! ለዚያውም ሳይሰነባበቱ ፡ ሳይነጋገሩ !
የፍቅርን እሳት በልብ ውስጥ አዳፍኖ መለያየት ! ሆዱን ባር ባር አለው ።

💥ይቀጥላል💥
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_አርባ


#ድርሰት_በትክክል_ገና

ከዚያም ትንሿ ልቧ ከውስጥ... በደስታ!!
እየዘለለች እየጨፈረች...እሷ ደግሞ ከላይ....እየተሸኮረመመች... እየተቅለሰለሰች ...እየተፍለቀለቀች .... ቀረበችው፡፡ ከቀኑ አስራ ሁለት ሰዓት ሆኖ ነበር::
በፍቅር መረታቷ ሌላው ችግር ቢሆንም፤ ሻምበል የምትወደው ታናሽ ወንድሟን ዋስ ሆኖ ያስፈታላት ባለውለታዋ ጭምር ነው::
“እጁን ለሰላምታ ዘርግቶ እንዳያሳፍረኝ ብቻ” እያለችና ጉንጩን ለመሳም የነበራት ምኞች እንዳይሰናከል እየፈራች ስትጠጋው! ሁለቱን እጆቹን ግራና ቀኝ ዘርግቶ ለእቅፍ ሲጋብዛት፣ ያለማንገራገር እዚያ ሰፊ ደረቱ መካከል ሄዳ ልክክ አለችበት። ሻምበል በአካባቢው ለሚታይ ሰው ደንታ ሳይሰጠው ለረጅም ጊዜ እንደተለያት ፍቅረኛው ቁልቁል ወርዶ
ጉንጯን ሳመችው። ከዚያም
ጉንጯን ሲስማት፤ እሷም አገላብጣ
ከንፈሯን ሊስማት በልቡ ውስጥ የነበረው ስሜቱን እንደምንም ተቆጣጠረና....
“ታዲያስ የኔ ቆንጆ” ሲላት፡፡
“ አለሁ ሻምበል” ብትለው፡፡
“ማዕረጉን ለሌላ ጊዜ ቢቆየንና በስሜ ብሩክ ብለሽ ብትጠሪኝስ?” በማለት
ካረማት በኋላ፤ እጅ ለእጅ ተያይዘው፤ ወደ ውስጥ ዘለቁ፡፡
ከዚያም አመቺ የሆነውን፤ ለግል ጨዋታቸው የሚስማማውን አካባቢ መርጠው፤ ተቀመጡ፡፡ ትህትና ልቧ በደስታ ዘለለች፡፡ ያ አምስት ቀን ሙሉ ሲያቃዣት የነበረው ፍርሃቷ ተወገደላት። በቀለበት ጣቱ ላይ ቀለበት ያለማድረጉን አረጋገጠች፡፡
“አዎን አምላኬ አላገባም ማለት ነው፡፡ ግን ማን ያውቃል ባለትዳር ለመሆን ቀለበቱ የግድ በጣቱ ላይ መኖር የለበትም እኮ?!
ወደሌላ ነገር ውስጥ ከመግባቴና ችግር ውስጥ ከመውደቁ በፊት ጥርጣሬዬን ማስወገድ አለብኝ፡፡ እጠይቀዋለሁ” በማለት ተጽናናች አመቺ ቦታ መርጠው፤ ለስላሳ እየጠጡ በሰፊው ሲጨዋወቱ አመሹ።
ሻምበል ወላጆቹ ከሱ የሚጠብቁ ባይሆኑም ሁለት ታናናሽ ወንድሞቹን
በማስተማር ላይ የሚገኝ ወንደላጤ መሆኑን አስቀድሞ ሲነግራት፤ እፎይ
አለችና እሷም ቀደም ብላ የጀማመረችለት የህይወት ታሪኳን በዝርዝር አጫወተችው፡፡
ፍርሀቱ ከተወገደላትና በፍቅር የወደቀችለት ሰው ከእንግዲህ
ወዲያ የግሏ ብቻ መሆኑን ካረጋገጠች በኋላ፤ ደስታዋ እጥፍ ድርብ ሆነ፡፡ ምሽታቸውም የማይጠገብ፤ ጨዋታቸውም የማይሰለች ፤እንደማር
እንደወተት የሚጣፍጥ ሆነ፡፡ ሻምበል ከእንግዲህ ወዲያ በጊዜያዊ ጓደኝነት ሳይሆን በህይወት እስካሉ ድረስ እስከ ወዲያኛው በትዳር ተሳስረው እንዲኖሩ ምኞቹን ሊገልጽላት ቢፈልግም፤ መቸኮል መስሎ ስለታየው ፤ "ግድ የለም በሌላ
ጊዜ እገልጽላታለሁ” ሲል በልቡ አምቆ ያዘው።

ከጣይቱ ሆቴል ሲወጡ ከምሽቱ ሁለት ሰአት ሆኖ ነበር ያውም ስለሰአቱ መምሸት እሱ ነው እንጂ እንደሷ ሁኔታ እዚያ ከሱ ጋር አፍ ለአፍ ገጥማ እያወራች ብታድር ምኞቷ ነበር፡፡እንዲያውም ስለሰዓቱ መምሸት ሲያሳስባት ትንሽ ንድድ ብላ
“ወይኔ ጉዴ መሸ” አለች ውሸቷን፡፡
“አይዞሽ እቤት ድረስ እሸኝሻለሁ” አላትና ተያይዘው ወጡ።
ከወዲያ ማዶ ካለው ቀይ መብራት ከሚበራበት መጠጥ ቤት ውስጥ አስር
አለቃ በሪሁን ደረቅ ጂን እየጠጣ ነበር፡፡
እሱ ነው ወይስ ሌላ?” በማለት ተጠራጠረና አንገቱን እንደስጎን ወደ
ውጭ አስግጎ አየው፡፡ አወቀው፡፡ ከጉኑ ያለችውንም ልጅ ለማየት ሞከረ ሻምበልና ትህትና ቁልቁል ወደ አሮጌው ቄራ የሚወስደውን ቀጭን የአስፋልት መንገድ ሲወርዱ እጅ ለእጅ ተያይዘው ፤ በፍቅር
ስሜት ደንዝዘው ፤ በደስታ እየዋኙ ነበር፡፡
ትህትና እቤት መድረሷን ሳታውቀው ነበር የደረሰችው:: ሻምበል ብሩክ ቆም አለ፡፡ ለመጨረሻ ጊዜ እንዴት አድርጎ እንደሚሰናበታት ጨነቀው::
“ደህና እደሪ” ብሉ
በእጅ ሊጨብጣት?
የማይታሰብ ነው።አሁን በደንብ ተለማምደዋልና፤ በናፍቆት ሲገናኙ ከነበረው በላይ በናፍቆት ሊሰነባበቱ እንደሚገባ ተሰማው፡፡ በዚህ በጨለማ ውስጥ የፍቅር አምላክ ቢያያቸው እንጂ፤ ሰው እንደማያያቸው ገመተ፡፡ የፍቅር አምላክ ቢያያቸው ደግሞ፤ ነፍስና ሥጋቸው ይፀድቃሉ እንጂ፤ አይኮነኑም፡፡
ሻምበል ይህ ተሰማውና ትንሿን ፍቅር መሥራት ፈለገ፡፡
ትህትናም በልቧ “አሁን እንኳን በዚህ ምሽት ፤በጨለማ ውስጥ፤ ሰው በሌለበት ፤ ሳይስመኝ ከሄደ ጨካኝ ወይንም ፈሪ መሆን አለበት” እያለች ታስብ ነበር፡፡
ይሄንን የውስጥ ስሜታቸውን፤ የፍቅር አምላክ በደመ ነፍስ አናበባቸውና፤ ሁለቱን እጆቿን በሁለቱ እጆቹ እንደያዘ ትንሽ ዘወር ቢያደርጋት፤ ሊያከሩት እንደዘወሩት እንዝርት አይነት ሆና ተሽከረከረችና ሄዳ በክንዱ ላይ ወደቀች፡፡ ከዚያም ወደ ላይ ቀና ሲያደርጋት፤ ሳታስበው አፏ ተከፍቶ፤ የሱን አፍ ፍለጋ ሄደ፡፡ ሻምበልም ወደ ደረቱ አስጠግቶ፤
በቀኝ እጁ የግራ እጅዋን በመያዝ፤ ወደ ላይ ሳብ ሲያደርጋት፤ በህዋ ላይ
እንደምትንሳፈፍ ዓይነት፣ መሬት የስበት ኃይሏን አጥታ ቆንጥጣ ልትይዛቸው እንዳቃታት ዓይነት ስሜት ተሰማት፡፡
ሻምበል ብሩክና እሷ መሬት ለቀው በመብረር ላይ ያሉ መሰላት፡፡ መላ ሰውነቷ በሱ ክንድ ላይ ወድቆ ወደኋላዋ ስትለጠጥና ረጅሙ ዞማ ፀጉሯ ወደ ኋላዋ ሲበተን ፊልም የምትሰራ ተዋናይ ነበር የምትመስለው....

ሻምበል በሷ ሁኔታ ተመሰጠና፤ እሱም አብሯት በስሜት ሰክሮ ወደዚያ እሷ ወዳዘነበለችበት ጉን ሲያዘነብል ከቤታቸው አጥር አጠገብ የቆመው የመብራቱ ምሰሶ እሷን በመደገፍ በኩል ተባበረው።
ትንፋሻቸው ቀስ በቀስ እየፈጠነ ትኩሳታቸው እጨመረ ሄደ፡፡ከዚያም እኒያን እንጆሪ ከንፈሮቿን ሲመጣቸው፤
የሱን እንኮይ ከንፈሮቹን ደህና አድርጋ ተመገበቻቸው። ለረጅም ጊዜ በዚህ ሁኔታ ላይ እንደቆዩ የሆኑ ሁለት መንገደኞች እያወሩ መጡ።
በዚህ ጊዜ ከዚያ ሰመመናዊ ስሜት ነቅተው አካባቢያቸውን ለማየት
ቢሞክሩ፤ ይህ ሁሉ ድርጊት የሚፈፀመው ጨለማ ውስጥ ቢሆንም በአደባባይ ላይ መሆኑን አሁን ገና ማሰብ ጀመሩ። ከዚያም ቀና ብላ ፊት ለፊት ሆነው ይተያዩ ጀመር። ሰዎቹ እያወሩ አለፉ።
ትህትና ልቧ ፈሰሰች፡፡ በቃ አልቻለችም፡፡ መለያየት ጨነቃት::
“እሺ ብሩኬ ደህና እደርልኝ እንባ እየተናነቃት፡፡
“እሽ ትህትናዬ ደህና እደሪልኝ” እሱም ዐይኖቹን ቡዝዝ አድርጎ እየተመለከታት፡፡ እግራቸው ሲንቀሳቀስ ልባቸው ግን በዚያች ቦታ ላይ የፍቅር አበባዋን ተከለች፡፡
ለዘለዓለም ሳይላቀቁ በዚያው ቢቆዩ ምንኛ ደስተኞች ይሆኑ ነበር? እንደዚያ ሆኖ ሳይላቀቁ መቆየት አይቻልምና ተላቅቀው ይተያዩ ጀምር፡፡ ሁለቱም በፍቅር ደንዝዘው፤ አንደበታቸው ስራውን እንዳቆመ ሁሉ የፍቅራቸውን መጠን የሚገልጹበት ቋንቋው አጠራቸውና፡-
“እወድሻለሁ ትህትና” ሲላት “እኔም በጣም እወድሃለሁ ብሩኬ”
አለቸው፡፡
ከዚያም ፊቷን አዙራ አንድ ሁለት እርምጃ ተራመደችና ዞር ብላ የመንገዱ መብራት ብርሀን በፈነጠቀበት ጨለማ ውስጥ አሻግራ ብታየው ሻምበል ብሩክ አፉን ከፍቶ በአድናቆት ሲያስተውላት አይን
ለዐይን ተጋጩ።
ለመጨረሻ ጊዜ እጆቿን አውለብልባ የአጥሩን በር ስትከፍት፤ እሱም እጆቹን አውለብልቦ፤ “በሰላም እደሪልኝ የኔ ቆንጆ” ብሎ ተሰናበታት፡፡
እንደ እውነቱ ከሆነ እጁ ብቻ ሳይሆን ልቡም በፍቅር አብራ ተውለብልባ ነበር.....

ከቤት እንደደረሰች ሰሞኑን በጊዜ መግባት የጀመረው ታናሽ ወንድሟ አንዱ አለም እናቱን እያጫወታት አገኘች። ከሻምበል ብሩክ ጋር ባሳለፈችው ሁኔታ በደስታ ፈንድቃ ስትገባ፤ ይኸውና አሁን ደግሞ ፀባዩ እየተቀየረ አስቸግሯት የነበረው ልጅ በጣም ተሻሽሎ፣ በጊዜ ገብቶ፣በሽተኛ እናቱን ሲያጫውት በማየቷ በደስታ ብዛት የምትሆነውን አጣች
ከዚያም እናቷንም እሱንም ሳመችና፤ የእጅ ቦርሳዋን ጣል ካደረገች
👍3
በኋላ ልብሶቿን ቀያየረች። የዛሬው ደስታ እውነተኛ ደስታ እንዲሆን፣ ቆንጆ እራት መስራት እንዳለባት ወሰነች፡፡
“አንዱዬ ተነስ ሥጋ ገዝተን እንምጣ” አለችው። አንዱ ዓለምም በደስታ ብድግ አለና ተያይዘው ወጡ፡፡
መደዳውን ከሚታዩት ልኳንዳ ቤቶች መካከል ከየትኛው እንደሚገዙ ለመወሰን ሲያማትሩ...
"ነይ ቆንጂት ምርጥ የሀረር ሰንጋ ነው” አላት አንድ ነጭ ካፖርት የለበሰ ወጣት የሉካንዳ ሠራተኛ የተሰቀለውን ስጋ በቢላዋ እየነካካ፡፡
መደዳውን የተሰቀሉት ብልቶች በሙሉ ሦስት መቶ ሻማ መብራት እላያቸው ላይ ነዶባቸው ያብለጨልጫሉ፡፡ አንዳንድ ሥጋ ቤቶች ሥጋውን ሆነ ብለው ቅባት ይለቀልቁታል፡፡ እንዲያብለጨልጭ...
እንዲያብረቀርቅ... ዐይን እንዲስብ፡፡ በቁም የትኛው ጥሩ ከብት እንደነበረ
የሚያውቀው አራጁ እንጂ ትህትናም ሆነች ወንድሟ በዚህ ረገድ ልምዱ
አልነበራቸውም፡፡ ወደ ጠራቸው ልኳንዳ ቤት ጎራ አሉ፡፡
“ልክ እንዳንቺ ቆንጆ ሥጋ ነው” አላት፡፡ መቼም ለገበያ ሲባል የማይሰጥ ምሳሌ የለም::
ሰውና ሥጋን እንዴት አመሳሰልከው እባክህ?” አለው አንዱአለም በቀልድ መልክ፡፡
“ልክ እንደናንተ ለዐይን ደስ የሚል፤ ሲበሉት ደግሞ ኬክ የሆነ ሥጋ ነው ማለቴ ነው” አለና ትንሽ ፈገግ በማለት እነሱንም ገበያውንም አንቆለጳጰሰ፡፡
“በል እስቲ ከሱ ከሽንጡ ሁለት ኪሎ” አለችው። በእውነትም ጥሩ ሥጋ ደህና አድርጐ ሳይሽቅባቸው ሰጣቸው፡፡ የዛሬው ቀን በእውነትም ልዩ ነው፡፡ የሥጋ ዘር ካዩ ድፍን አሥራ አምስት ቀናቸው
ነበር፡፡
ያንን ሥጋ በልዩ ልዩ ዓይነት ሠራችው። እጅ የሚያስቆረጥም አድርጋ እየተጨዋወቱ ፤እየተጎራረሱ፤ ከተመገቡ በኋላ ሊተኙ አካባቢ...
“ብሩኬ ይዘሽው ነይ ብሎኛል እኮ!” አለችው ለአንዱዓለም፡፡
“ብሩኬ” የሚለው ቁልምጫ ምን ማለት እንደሆነ ወዲያውኑ ገባው::
እንደ እውነቱ ከሆነ ትህትና ሻምበል ብሩክን ብታገባው የሚል ስሜት ካደረበት ውሎ አድሯል፡፡ ያንን ሲኦል የሆነ እስር ቤት ደግሞ አድሮበት ቢሆን ኖሮ ምን አይነት የሞራል ውድቀት ይደርስበት
እንደነበረ ሲያስበው ይዘገንነዋል፡፡ እነዚያ ቢወረወሩ ሰው የሚፈነክቱ እንደ ጥጥ ያባዘቱት ተባዮች ደም እንባ አስለቅሰውታል። ክርፋቱ አይረሳውም ፡፡ከዚህ ሁሉ ነጻ ያወጣው ሻምበል ብሩክ ነው፡፡ ግርማ ሞገሱ የሚያኮራው፣ ደስ የሚል፤ ሳቂታውና፤ ተጫዋቹ ሻምበል ብሩክን ልቡ ስለወደደው፤ እህቱ ብታገባውና፤ የቤተሰብነት ዝምድናን ቢመሰርቱ ደስታው ወደር አልነበረውም::
ሻምበል ብሩክና ትህትና በጣይቱ ሆቴል ሆነው ሲጨዋወቱ
ያልተወያዩበት ርዕስ አለ ማለት አይቻልም፡፡ በተለይ ስለጓደኛዋ አዜብና
ስለአንዱ ዓለም ስታጫውተው በሚቀጥለው ፕሮግራማቸው ላይ
ሁለቱንም ይዛቸው እንድትመጣና የምሳ ግብዣ እንደሚያደርግላቸው ነግሯታል፡፡
ከሻምበል ብሩክ ጋር የፍቅር ሀሁ መጀመሯን፤ ከዚያም በላይ እዚያ አጥራቸው አጠገብ ምን እንዳደረጉ ሁሉ ለአዜብ ልትነግራት ቸኩላ ነበር።
መቼ ነው ይዘሽው ነይ ያለሽ?” አላት አንዱዓለም በጉጉት፡፡
የዛሬ ሣምንት የትም እንዳትሄድ እሺ? የምሳ ግብዣ አለህ” አለችው፡፡ አንዱዓለም በጣም ተደሰተ፡፡ ቀጠሮው ናፈቀው፡፡ ከዚያም እሱ ወደ ድንክ አልጋው ሲሄድ እሷ ደግሞ ወደ እኗቷ አልጋ ሄደች፡፡
ጠዋት ወደ ሥራ ከመሄዷ በፊት ለአዜብ ስልክ ደወለችላት፡፡
“ልነግርሽ አልችልም በቃ ሆነ!” በሳቅ እየተፍነከነከች፡፡
ትሁቲና አትይኝም!” አዜብ በነገሩ ተደንቃ ጠየቀቻት፡፡
“አዜቢና ሙች! ልክ እንዳልነው”
“ውይ ታድለሽ ትሁት” የበለጠ አደነቀችላት። ስለነበረው ሁኔታ ጫፍ
ጫፉን ነገረቻት፡፡
ትህትና አንድ አጋር በማግኘቷ፣ የኑሮ ቀንበር ያጎበጠው ወገቧን ቀና
የሚያደርግላት፤ ስታዝን፤ ስትተክዝ፤ አለሁልሽ የሚላት አለኝታ በማግኘቷ አዜብ ደስታውን አልቻለችም።
“አዜቢና ሳምንት የምሳ ግብዣ አለሽ ! አስተዋውቂኝ ብሎኛል፡፡ ሌላውን
ደግሞ ሀሙስ ዕለት እቤት መጥቼ አጫውትሻለሁ። ቻዎ!”
እሽ ትሁት በናፍቆት እጠብቅሻለሁ፡፡ ቻዎ!” ያንን እስከ ዛሬ ድረስ ለማንም ተሸንፎ የማያውቀውን የጓደኛዋን ልብ ለመጀመሪያ ጊዜ ማሸነፍና መማረክ የቻለውን ሰው ለማየት ጓጓች....
በሥራ ላይ ከቆየች በኋላ የምሳ ሰዓት ሊደርስ አካባቢ አበራን አስፈቅዳ ወጣችና ለሻምበል ብሩክ ስልክ ደወለችለት፡፡ በስልክ ተጨዋወቱ፡፡ በቃ ፍቅር ሥሯን እየሰደደች መጣች፡፡ ድምጹን ካልሰማች
ቅር ቅር ይላት ጀመር፡፡ በየደቂቃው ብትሰማው ምንኛ ደስ ባላት? እሱም
ሳምንቱን ሙሉ ሲደዋወሉ ከቆዩ በኋላ ክፉኛ ተነፋፍቀው፤ የቀጠሮአቸው ቀን ደረሰላቸው፡፡ አዜብና አንዱአለም የዛሬው የክብር እንግዶች በተደረገላቸው ጥሪ መሰረት አብረዋት ሄዱ።
ቀጠሮአቸው በጥሬ ሥጋና ጎድን ጥብስ ዝግጅቱ በታወቀው በመተባበር ሆቴል ነበር። በዚያን ዕለት ሻምበል ብሩክ ሱፍ ለብሷል፡፡ ክራቫትም አስሮ ነበር። አቦ እንዴት ነበር ያማረበት? ትህትና ስታየው
የበለጠ በደስታ ሰከረች። የደንብ ልብሱ ብቻ መስሏት ነበር፡፡ ይሄኛው ደግሞ ጭራሽ ልዩ ሆነባት፡፡ ሄዳ እቅፉ ውስጥ ስትወድቅ በከንፈሩ ተቀበላት።
ፍቅራቸው ገደብ አጣና፤ በጓደኛዋና በወንድሟ ፊት ሳማት፡፡
ደንታም አልሰጣቸው፡፡ አዜብና አንዱአለም ትንሽ እንደማፈር ብለው ማዶ
ማዶውን አዩ።
ባልሳሳት አዜብ ነሽ” ቀልጠፍ ብሎ እጁን እየዘረጋላት፡፡
አልተሳሳትክም አዜብም ሳቅ እያለች።
“አንዱ ዓለም ጋር እንኳ በሚገባ እንተዋወቃለን” እቅፍ አደረገው።
አንዱዓለም ደስ አለው። ብቻ ሻምበል ብሩክ ሳቂታና ተጫዋች ስለሆነ
የሰውን ልብ በቀላሉ የመማረክ ችሎታ አለው፡፡
የሀረር ሰው ለሳቅና ጨዋታ የታደለ መሆኑ ይነግርለታል፡፡ለዚህ ነው መስል፤ ሻምበል የዚህ ዓይነት ባህሪ ይንፀባረቅበታል።
አይከብድም፡፡ አዜብም አንዱዓለምም በሱ ሁኔታ ነፃነት ተሰማቸው።አዜብ በዝና ከምታውቀው የበለጠ የምታየው ሻምበል ብሩክ ማረካት፡፡
“እንዴት ዓይነት እድል ነው የገጠማት?” በጓደኛዋ ጥሩ ዕድል ቀናች፡፡
ለምን እንደቀናች ግን እሷም አልገባትም። የምትወዳት ጓደኛዋ ናትና።
ብሩክ ወዲያውኑ “አዜቢና” እያለ መጫወት ጀመረ፡፡ የቁልምጫን ስም በአንድ ቀን መጥራት ይከብዳል፡፡ ለብሩክ ግን ይህ ቀላሉ ነው፡፡
ሁሉም ነገር በሚያስደስት ሁኔታ ቀጠለ፡፡ ጨዋታና ሳቁ ደራ። ፍቅር በፍቅር ሆኑ።
ትህትና ይህንን የመሰለ ጠንበለል የሰጣት አምላክ ችግሯን አይቶ ሊክሳት መሆኑን አመነች። በዚህ መሃል አንዱአለም እስር ቤት የገባበት ምክንያት በርዕስነት ተከፈተና መወያየት ሲጀምሩ.

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
አትሮኖስ pinned «#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ ፡ ፡ #ክፍል_አርባ ፡ ፡ #ድርሰት_በትክክል_ገና ከዚያም ትንሿ ልቧ ከውስጥ... በደስታ!! እየዘለለች እየጨፈረች...እሷ ደግሞ ከላይ....እየተሸኮረመመች... እየተቅለሰለሰች ...እየተፍለቀለቀች .... ቀረበችው፡፡ ከቀኑ አስራ ሁለት ሰዓት ሆኖ ነበር:: በፍቅር መረታቷ ሌላው ችግር ቢሆንም፤ ሻምበል የምትወደው ታናሽ ወንድሟን ዋስ ሆኖ ያስፈታላት ባለውለታዋ ጭምር ነው::…»
Forwarded from አትሮኖስ (፲፬)
👉 ሴት በወር አበባዋ ጊዜ መጸለይ ትችላለች?
👉​​ ግለ አውናን / ሴጋ /ማስተርቤሽን/ የፈጸመ ሰው ተክሊል ማግባት ይችላልን?
👉 በሱባኤ ወቅት ህልመ ሌሊት (ዝንየት) ቢመታን ምን እናደርጋለን?
👉 ሕልመ ሌሊት በራሱ ኃጢአት ነውን?
👉 ሕልመ ሌሊት በምን ይከሰታል?
👉 ከዝሙት አጋንንት እና ከዝንየት በተጨማሪ በሕልመ ሌሊት የሚፈትነን አጋንንት የትኛው ነው?
👉 የሕልመ ሌሊት መፍትሔ ምንድን ነው?

በእነዚህ ትምህርቶች ዙርያ እየተማማርን እንገኛለን እርሶም እውቀቱ እንዲኖርዎ ከፈለጉ ይህን መስፈንጠርያ ይንኩ👇



https://xn--r1a.website/joinchat/9UhoYGd7ODFhMmM0
https://xn--r1a.website/joinchat/9UhoYGd7ODFhMmM0
1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሀያ_አንድ


#ድርሰት_በትክክል_ገና


ውድ አንባብያን ከላይ በለቀቅናቸው ሁለት ክፍሎች ላይ ማለትም 39, እና 40 ያልነው በስተት ነው ክፍል19 እና 20 ናቸው ስለተፈጠረው ስተት ይቅርታ እየጠየቅን በቀጣዩ ክፍሎች ላይ እናስተካክላለን..የቁጥር ስተት ብቻ ነው እንጂ የክፍል መቆራረጥ የለውም። መልካም ንባብ።
=========================
....“እኔና አንተ ሌላ ቀጠሮ ይኖረናል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ሰፋ አድርገን
እንወያያለን እሺ?” አለው፡፡ አንዱ አለም በደስታ ተቀበለው። ርዕሱ ተቀየረ፡፡

ምሳው አብቅቶ የሚጠጣ ነገር ሲታዘዝ፤
አንዱአለም ቢራ፤ አዜብና ትህትና ደግሞ ጭማቂ፤ አዘዙ፡፡ በወንድሟና በጓደኛዋ ፊት በመሆኑ እንጂ ከሻምበል ጋር ብቻ ብትሆን ኖሮ በዛሬው የፌሽታ ቀን ቢራ ትጠጣ ነበር፡፡ እድሜ ለዶክተር ባይከዳኝ ቢራ አለማምዷታል፡፡
ሻምበል ብሩክ ለትህትና የሆነ ነገር በጆሮዋ ሹክ አላት::
እንዲያ ወደ ጆሮዋ ጠጋ ብሎ ፤ በግራ ክንዱ ትከሻዋን እቅፍ አድርጎ፤አዜብ ስትመለከት በድጋሜ ቀናች፡፡ እንደዚህ ያፈቀረችው እና ያፈቀራት ሰው አጋጥሟት አያውቅም፡፡ የሷ ጓደኞች የሳምንት ግፋ ካለ የአንድ ወር ብቻ ናቸው፡፡ ችግሩ ከማን እንደሆነ እራሷን እየጠየቀች እስከዛሬ ድረስ መልስ ያላገኘችለት ጉዳይ ነው፡፡ አብዛኞቹ “አዜቢና አዜቢና” እያሉ
እያቆላመጡ ይጠጓትና፤ ከአንድ ቀን ግብዣ በኋላ በሁለተኛው ቀጠሮ
ላይ ጨርቅ ተጋፍፈው፤ በዚያው እብስ ብለው ይጠፋሉ፡፡ እንደውነቱ ከሆነ እሷም ወረተኛ ነች፡፡ በተለይ መኪና ላለው ወንድ ልቧ ይደነግጣል። ለሚያዝናና፤ ለሚያንሸረሽር፤ ልቧ ክፍት ነው። እግረኛው ብዙም አይስባትም፡፡

“አዜቢና ከቦይ ፍሬንዷ ጋር ለምን አልመጣችም?” በማለት ነበር ሹክ ያላት፡፡ ትህትና ሣቅ አለችና...
“ በሚቀጥለው” አለችው፡፡ የሚያወሩት ስለእሷ እንደሆነ ጠርጥራ አዜብ
ትህትናን ጠቀሰቻት፡፡ እሷም መልሳ ጠቀሳቻት። ተጠቃቀሱ። አዜብ
ስለእሷ የምታውቀውን ያህል እሷም ስለአዜብ ታውቃለች፡፡
የሆቴል ልብስ የለበሱት አስተናጋጆች በጎደለ ለመሙላት ሽር ጉድ ይላሉ፡፡ ሻምበል ብሩክ እናቷን ለመጠየቅ መፈለጉን ገልጾ ያሳወቃት ወደ ማምሻው ላይ ነበር፡፡ ሻምበል ይህንን ያልጠበቀችውን እጅግ አስደሳች
የሆነ ሀሳብ ሲያቀርብላት በደስታ ተውጣ ቀና ብላ አየችው:: ፈገግ አለና
ወደ ጎን ተመለከታት፡፡
“ተያይዘን ወደ ቤት” አላት፡፡ ለዚህ ንግግሩ ካሳ ከንፈሩን መሳም ነበር፡፡ምን ያደርጋል? አይመችም።እያማራት፤ ተወችው::
"አይመሽብሽም አዜቢና" አለቻት ጓደኛዋን፡፡
“አይመሽብኝም" አለች ቶሎ ልትለያቸው ስላልፈለገች። በሻምበል ብሩክ ሀሳብ አዜብና አንዱአለም እጅግ ተደሰቱ፡፡ አንዱ አለም እስር ቤት ገብቶ ያደረ ዕለት ትደነግጣለች ብላ ከደበቀቻት በኋላ ሻምበል ብሩክ የተባለ ሰው ዋስ ሆኖ ያስፈታው መሆኑን ለእናቷ የነገረቻት፤ አንዱ አለም በሽተኛን ለመጠየቅ
ተፈትቶ እቤት ሲገባ ነበር፡፡ ከዚያን ቀን በኋላ ግን ስለ ሻምበል ብሩክ
ያልተወራበት ቀን አለ ለማለት ያስቸግራል።
በሆነው ባልሆነው የሻምበል ብሩክ ሥም እንደ ዳዊት ሲደገም እናቷ ጠርጥራለች፡፡ በዚህ ምክንያት ወ/ሮ አመልማል ሻምበል ብሩክን በመልክ ባይሆንም በዝና አውቃዋለች ማለት ይቻላል።
በሽተኛን ለመጠየቅ
ተፈትቶ እቤት ሲገባ ነበር፡፡ ከዚያን ቀን በኋላ ግን ስለ ሻምበል ብሩክ
ያልተወራበት ቀን አለ ለማለት ያስቸግራል።
በሆነው ባልሆነው የሻምበል ብሩክ ሥም እንደ ዳዊት ሲደገም እናቷ ጠርጥራለች፡፡ በዚህ ምክንያት ወ/ሮ አመልማል ሻምበል ብሩክን በመልክ ባይሆንም በዝና አውቃዋለች ማለት ይቻላል።በሽተኛን ለመጠየቅ በሚል ሰበብ ሻምበል ብሩክ ለእናቷ ያልገዛው ነገር የለም። ሥጋው፣ አትክልቱ፣ ለስላሳው፣ ኬኩ ይህንን ሁሉ ገዝተው ተሸክመው እቤት ሲደርሱ ሠራተኛዋ መጥታ በሩን ከፈተችላቸው፡፡ ልጅቷ በሻምበል ብሩክ ላይ ዐይኖቿ ተተክለው ቀሩ፡፡ግርማ ሞገሱ ያስፈራል። ከዚያም ትህትና ቀደም ብላ ወደቤት ገባችና ቤቱን ትንሽ ለማዘጋጀት ጥረት አደረገች። ጠንቃቃና ጽዳት ጠባቂ
ስለሆነች መዝረክረክ አይታይም ነበርና ብዙም አልተቸገረችም፡፡
እማዬ እንግዳ መጥቷል” ብላ ለእናቷ ሹክ ስትላት ማን መጣ ትሁቴ?” ደንግጣ ከተኛችበት ቀና ለማለት ተንደፋደፈች።
ብርድ ልብሱን እያለባበሰቻት፡፡
ወዲያው ሦስቱም ተከታትለው ገቡና ከእንግዳ ማረፊያው ከሶፋ ወንበሩ ላይ አረፍ አሉ። ቤቱ ንጹህና ቅልል ያለ ነበር፡፡ ሻምበል ዙሪያ ገባውን ተመለከተ፡፡ በትልቅ መስታወት ውስጥ ከነግርማ ሞገሱ የሚያየው ፎቶ የአባቷ እንደሆነ ገመተ፡፡ በቤቱ ንጽህናና አያያዝ ልቡ
ተማርኮ...
“የኔና የትሁት ጎጆም እንደዚችው ...” ሲል አሰበ። ትህትና ከደስታዋ ብዛት የምታደርገውን አታውቅም፡፡ የምትይዝ የምትጨብጠው ጥፍት ብሎባታል፡፡

“ሻምበል ብሩክ ነው አይዞሽ” ::
“ብሩኬ ና ወደዚህ” መጣችና እጁን ሳብ አድርጋ ካስነሳችው በኋላ ወደ እናቷ የምኝታ ክፍል ይዛው ገባች፡፡
ወ/ሮ አመልማል ሻምበል ብሩክን እንዳየችው ወደደችው። በቃ ልቧ ያለማመንታት አማችነቱን ተቀበለው። ልጅዋ ፍርጥ አድርጋ ባትነግራትም፤ እሷም ኮረዳ ሆና ባሳለፈችበት ዘመን ውስጥ የድብቅ ፍቅር ምልክቶች ምን ምን እንደሆኑ ቀምሳዋለችና፤ ልጅዋ በሻምበል ብሩክ መረታቷን በቀላሉ እንዳወቀች፤ ከወደደችው ሰው ጋር በወግ
በማዕረግ በትዳር እንድትኖር ምኞቷ ሆነ፡፡
ከዚህ ሁሉ የበለጠው ደግሞ፤ ይዛ የመጣችው ሰው ልብ የሚያስደነግጥ ለግላጋ ወጣት መሆኑን ስትመለከት፤ በደስታ ፈነጠዘች፡፡

“ጤና ይስጥልኝ እናቴ” ሄዶ ጉንጮቿን በተኛችበት ሳማት፡፡
ወ/ሮ አመልማል በዚያን ሰዓት የተሰማትን ስሜት መግለጽ አስቸጋሪ ነው። የሆነ ስሜት የሆነ የደስታ ሲቃ ተናነቃት፡፡

ለመጀመሪያ ቀን የምታየው ጠንበለል ወጣት፤ እሷን እዚያ ለረጅም ጊዜ ከአልጋ ያልተነሳችውን ገመምተኛ፤ ልክ እንደ እናቱ ሄዶ እቅፍ ድግፍ አድርጎ ሲስማት፤ ከልጆቿ አንዱ እንጂ፤ ፍጹም ባዳ ነው
ብሎ ማመን አቃታት፡፡
ይህ ለሷ ከብዶ ታያት እንጂ ፤ ለሻምበል ብሩክ ተወዳጅነትን ካተረፉለት መልካም ባህሪዎቹ አንዱ ነበር፡፡ ሰውን ትንሽ ትልቅ በማለት የማይንቅ፤ የታሰረ የታመመ መጠየቅ የሚወድ ሰው ነው። እሷም
ጉንጬን ሳመችው። እነሱን ስትመለከት የትህትና ልብ በደስታ ዘለለች::አቤት የተሰማት ደስታ!
“አይ ብሩኬ ምን ዓይነት ወርቅ ሰው ነህ?” ብሩክን በልቧ አደነቀችው::
ሻምበል ብሩክ ከዚህ በፊት የኖረ ዘመድ መስሎ ቁጭ አለ::
የመጣለትን ወንበር ትቶ እዚያ አልጋው ጫፍ ላይ አጠገቧ ቁጭ ብሎ
ራሱን ካስተዋወቀ በኋላ፤ ስለበሽታዋ፤ ስለኑሮዋ ስለወደፊቱም ፤ እያነሳሳ ሲያጨዋውታት፤ ከላይዋ ላይ የተገፈፈላት ያህል ተሰማትና፤ በሻምበል ብሩክ ሁለንተና ተመስጣ ጨዋታ ቀጠለች።

አዜብ ስለመሸባት ተሰናብታቸው ወደ ቤቷ የሄደችው የግዷን ነበር ማለት ይቻላል። የሻምበል ብሩክን ሁኔታ ያየ እንግዳ ነው ብሉ ለመናገር ይቸግራል፡፡ በአንድ ጊዜ ቤተኛ ሆኖ ቁጭ አለ። በዚህ ሁኔታ
ሲጨዋወቱ ካመሹ በኋላ ተሰናብቶ ሲወጣ፤ ከወንድሟ ጋር ሆነው
ሸኙት፡፡ ከዚያች ቀን በኋላ ሻምበል ብሩክ ቤታቸው ቤቱ ሆነ።
ከተቀጠረች ሁለተኛ ሳምንቷን ይዛለች፡፡ በእርግጥም ማለፊያ የገቢ ምንጭነቷና ገዳምነቷ ከወዲሁ እየታየ ነው፡፡ ከወትሮው ለየት ባለ ሁኔታ የደንበኞች ቁጥር እየጨመረ ነው።
እዚያ ለገበያ ገብቶ በመጀመሪያ እሷን እንደ ሽንኩርት በዓይኑ ሳይልጣት ወደ መጣበት ጉዳይ የሚመለስ መቼም ጥቂቱ ነው። የዕድሜ አቻዎቿ ብቻም ሳይሆኑ የአሮጊቱ የሽማግሌው
👍21
ዐይን ከላይዋ ቶሎ አይነቀልም።

እሷም ይህንን በዐይን የመላጡን አደጋ እየተለማመደችው ስለሄደች አሁን አሁን ሲያይዋት ማቀርቀርን እየተወች መጥታለች፡፡ሊያሻት ሊተሻሻት የሚፈልገውን በፀባይ የመሸኘት ልምዱንም አዳብራለች::

“ይብላኝ እዚያ ቡና ቤት ውስጥ ተቀጥረው ለሚሰሩ” እያለች ሁሉንም በፀባይ ታስተናግዳለች፡፡ ከዚህ ሁሉ ውስጥ ግን አንድ ሰው ብቻ በቀላሉ በፈገግታ ግብዣ የሚሽኝላት አልሆነም :: ከዚያም አልፎ በግል ህይወቷ ውስጥ እስከመግባት የሚደርስ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጾ አስፈራርቷታል።
ይህ የማትጋፋው ባላንጣ፤ በቤቱ ውስጥ የፈላጭ ቆራጭነት መብት አለኝ የሚለውና፤ በአባቱ ሀብት ስለሚመካ ከሥራ ያስወጣናል እያሉ ሰራተኞች የሚፈሩት እንደሻው ነበር።
“ምን የመሰለች ልጅ መለሰችህ ዛሬ ሽሜው የቀጠረው” ብሎ አበራ የነገረው እለት እንደዋዛ ነበር ያዳመጠው። የዚያን ያክል ትሆናለች ብሎ መገመት ቀርቶ አላለመውም። ትህትናን ያያት ሥራ በጀመረች በሣምንቷ ነበር።
ገና የሱቋን በር አልፎ ወደ ውስጥ እንደገባ፤ ያዩት እስከሚያፍሩበት ድረስ በቆመበት ቦታ አፉን ከፍቶ ቀረ፡፡ በሃሳቡ
እንደአውራ ዶሮ ሲከመርባት... ከዚያም በጭኖቿ መካከል ያለውን ሚስጥር ሲፈትሽ... ታየው። ምራቁን ዋጠ፡፡
“በደቂቃ ለጥብስ አደርሳታለሁ” አለ በልቡ፡፡ ለሚያዩት ሠራተኞች ደንታም ሳይሰጠው፤ በቀጥታ ደረቱን ነፍቶ ወደ ትህትና ሄደ፡፡

ይቀጥላል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2
አትሮኖስ pinned «#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ ፡ ፡ #ክፍል_ሀያ_አንድ ፡ ፡ #ድርሰት_በትክክል_ገና ውድ አንባብያን ከላይ በለቀቅናቸው ሁለት ክፍሎች ላይ ማለትም 39, እና 40 ያልነው በስተት ነው ክፍል19 እና 20 ናቸው ስለተፈጠረው ስተት ይቅርታ እየጠየቅን በቀጣዩ ክፍሎች ላይ እናስተካክላለን..የቁጥር ስተት ብቻ ነው እንጂ የክፍል መቆራረጥ የለውም። መልካም ንባብ። ========================= ....“እኔና…»
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

ጊዜ መደፊት አይገፈትርም።ጊዜ ለሰው ጭንቀትም ሆነ ደስታ ደንታ የለውም።
የራሱን ሥርዓት ጠብቆ የሚጓዘው፤ያለፈ ጊዜ አይመለስም ፤የወደፊቱ ደግሞ እንደ
ፈለግጉት ፈጥኖ አይመጣም። ሰው በጊዜ ቁጥጥር ሥር ነው እንጂ ጊዜ በሰው ቁጥጥር ስር አይደሉም ሰዓት ሰው ሠራሽ ነገር ነው ፤ ሞላውን በማዞር ካለበት ሰዓት ወይም ደቂቃ ማስቀደም ይቻላል ። የቀን መቁጠሪያም ሰው ሠራሽ
ነገር ነው ፤አንዱን ወር አልፎ ሌላውን ወር ማየት ይቻላል ።ቀንን ገፍቶ ማስመሸት፣ ወይም ምሽት ጎፍቶ ማንጋት ግን
የማይቻል ነው ።

አቤል ቢቸግረው እንዲህ አይነት የጊዜ ምርምር ውስጥ ገባ ። ችግሩ ነው ምርምሩን የጋበዘው ቀኑ አልመሽልህ "
ሌሊቱ አልነጋልህ እያለው ተቸገረ ለሌላው ተማሪ የዕረፍት ጊዜ ለእሱ ግን የመጨረሻው ደረጃ የጭንቀት ጊዜ
ሆኖበታል ። ቀንም ይተኛል ፡ ማታም ይታኛል ። ነገር ግን እንቅልፍ አይወስደውም ። እንዲሁ አልጋው ላይ እየተገላበጠ በሐሳብ መብከንከን ሆነ ። ጊዚ ከመቼውም ይልቅ የኋሊት እየተጎተተ የሚያቃስት መስለው ።

ሳምሶን ለዕረፍቱ ወደ ቤቱ ስለ ሔደ መኝታ ክፍላቸው ውስጥ የቀሩት አቤል ፡ እስክንድርና "ድብርት ” ብቻ ነበሩ ። “ ድብርት ” ፈተና ካለቀ በኋላ ያሳየው ለውጥ ቢኖር አልጋ ማንጠፉ ብቻ ነው ። በተረፈ እንደ ጥንቱ “ድብርት ጥናቱም ቢቀር ያው አልጋውን በጋቢ ጋርዶ በራሱ ሕልም ውስጥ መኖሩን አልተወም ። ወደ ውጭ ቢወጣ ብቻውን ነው ።

እስክንድር የዕረፍት ጊዜ ጓደኛው መጽሐፍ ነው ።የአማርኛና የእንግሊዝኛ ልብወለድ መጽሐፎችን እየተዋሰ
ሲያነብ ስለሚውል፥ ቀኑ በፍጥነት ነው የሚገሰግስለት ማንበብ ስልቸት ሲለው፡ወደ መዝናኛው ክበብ እየሔደ ቼዝ
ይጫወታል ። መቼም ከሱ ቦታ ሰው ቢጠፋ ሚስተር ሆርስ አይጠፋም ።

እስክንድር በዚህ ሁኔታ የዕረፍቱን ጊዜ ቢያሳልፍም ከአቤል ጋር አብሮ መጨነቁ አልቀረለትም ። ዐቅሙ በሚፈቅደው መጠን አቤልን ለማዝናናት የማያደርገው ሙከራ የለም ። ከአነበባቸው መጽሐፎች ውስጥ ጥሩ የሚላቸውን መርጦ ይሰጠዋል ። አቤል ግን ነጻ ኣዕምሮ ስለሌለው፥ አንዱንም ከነጣዕሙ አንብቦት አያውቅም ። ጀምሮ ሳይጨርሰው ይቀራል ። ወይም በግል ሐሳቡ ውስጥ እየዋዠቀ ገጹን
በመቁጠር ብቻ ይጨርሰዋል ። እስክንድር ወደ ቼዝ መጫወቻው ቦታ ሲሔድ አቤል አብሮት እንዲሔድ ለማድረግ ቢሞክርም እሺ አላለውም ፡ ከሚስተር ሆርስ ጋር ከተጣላ ወዲህ የመዝናኛ ክበቡን ረግጦት አያውቅም ።
አቤል ወደ ውጭ ብቅ እያለ ከሰዎች ቢቀላቀል ፡ ጊዜውን መዝናኛ ቦታዎች እየሔደ ቢያሳልፍና በአንዳንድ እን
ቅስቃሴዎች ቢሳተፍ፡ ጭንቀቱ እንደሚቀልለት እስክንድር
ቢረዳም ፡ ይህን ለማድረግ ሁኔታዎች አልተመቻቹለትም አብዛኛው መዝናኛ ገንዘብ ይጠይቃል ። ይህን ማሟላት
አይችሉም ። ገንዘብ በማይጠይቅበት መዝናኛ ቦታ ለመዋል ደግሞ የአቤል ሙሉ ፈቃደኝነት አይገኝም ። ሌላ ቀርቶ
ከእስክንድር ጋር ከሚያወራበት ጊዜ ይልቅ፡ ብቻውን ተደብሮ ውስጥ ውስጡን ነገር ሲያብሰለስል የሚውልበት ጊዜ
ይበልጣል ።

ትዕግሥት በተለያየ መልክ በሕልሙ እየመጣች ትታየዋለች ። አንዴ ይጣላሉ ፤አንዴ ጥላው በመሔዷ የተሰማውን ቅሬታ ይገልጽላታል ፤ አንዳንዴ ደግሞ ደብረ ዘይት ድረስ ሔዶ ሲገናኛት ያድራል ቀን ያሰበውን ማታ በሕልሙ ይደግመዋል አንዳንዴ በቅዠት ይወራጫል ።
ከትዕግሥት ናፍቆት ጋር ተደርቦ የወላጆቹ በተለይም የእናቱ ሁኔታ ፊቱ ላይ እየተደቀነበት መጨነቁ አልቀረም ።
ያስብ ያስብና ሁሉም ነገር ፍቺ የሌለው እንቆቅልሽ ይሆንበታል ። ሆኖም እንቆቅልሽ ነው ብሎ አይተወውም ።

ተመልሶ በዚያው ሐሳብ ዙሪያ ይሽከረከራል ፡ በሐሳብ ከመብከንከኑ ጋር የምግብ ፍላጎቱም እየቀነሰ ስለመጣ
በጣም ከስቶ ነበር ። ግን ለዚህ ደንታ አልነበረውም ። አካሉ መንምኖ ነፍሱ ብቻ ከውስጥ ሚን ሚን እስክትል ይጠብቃታል

ብርቅነሽ ትዝ ስትለው የደስታ ብርሃን ትፈነጥቃለች ።ስለ እሷ ማሰብ ደስ ይለዋል። አብሯት ካደረ ጀምሮ የመውደድ ስሜት ተቀርጾበታል ። የፍቅሩን ዐይነት ግን በግል ለይቶ ማወቅ አልቻለም ። ትዕግሥትን ይወዳታል ፡ ብርቅነሽን ይወዳታል ። የመወደዱ ዐይነት ይለያያል ሲያስቡት ደስ የሚልና ሲያስቡት የሚያስቃይ ፍቅር ! ስለ ብርቅነሽ ማሰብ ያስደስተዋል ፤ አያሠቃየውም ፤ ጭንቅላቱን አይበጠብጠውም ። ስለ ትዕግሥት ማሰብ ግን ያሰቃየዋል፥
ይበጠብጠዋል ፤ ያስለቅሰዋል ። እንዲያም ሆኖ ፍቅሩ ለምታሠቃየው ለትዕግሥት ያደላል ። ሙሉ ልቡን ያሳረፈው በትዕግሥት ላይ ነው ። ቀርቦ ምስጢሩን ካካፈላት ፥ ገላዋን ካቀፈውና ትኩሳቷን ሲቀበል ካደራት ሴት ይልቅ ከዐይኑ ላላለፈች ሴት ፍቅሩ ማመዘኑ ለምን እንደያነ ሊገባው አልቻለም ። “ የፍቅር ምስጢሩ ምንድነው ? ሲል አሰበ "
ፍቅር የሚወደው ሥቃይን ይሆን እንዴ ? ?

አንድ ቀን ብርቅነሽን ሲያስታውስ ከውስጡ “ሔደህ እያት ” የሚል አንዳች ግፊት መጣበት። ለእስክንድር ሳያማክረው ተደብቆ ብቻውን ሔደ ። ለምን እንደሚሔድና ቢያገኛት ምን እንደሚላት አላሰበበትም ። ገብቶ ለመጫወትም ቢሆን ፥ የሚጠጣ! ለማዘዝ በኪሱ ገንዘብ የለም ። እናም ቡና ቤቱ አጠገብ ሲደርስ ቀጥ ብሎ ቆመ።

የቡና ቤቱ በር ክፍት ነው ። ነገር ግን ድምፅ አይሰማበትም። እንደዚያ ዕለቱ ምሽት ሙዚቃና የሰው ቻቻታ የለበትም ። ከዝንቦች እምታ በቀር ጸጥ ረጭ ብሏል ።
መግባት አልደፈረም ። እየተንጎራደደ ሰው ብቅ እስኪል ይጠብቅ ጀመር ። ጥቂት እንደ ቆየ ፥ አንዲት ሴት የከሰል
ምድጃ ይዛ ከውስጥ ብቅ አለች ። አለባበሷ ግድ የለሽ ነው ።
ሻሿን የገርዳሳ አስራለች ።

አቤል ሲያያት ክው አለ ። የዋህነቷንና ጥሬነቷን አይታ የቡና ቤቷ ባለቤት ማታ ማታ እንደ አሻሻጭ ቀን ደግሞ እንደ ገረድ ነው የምትጠቀምባት ፡ ከሰሉ እንዲቀጣጠልላት ምድጃውን ወደ ንፋስ አድርጋ ቀና ስትል አየችው ቶሎ አልለየችም። ያው እንደ መንገደኛ ነበር የተመለከተችው ። ስታየው ተደናግጦ ጀርባውን ሰጥቷት ወደ ኋላው ሊመለስ ፈልጎ ነበር ። ግን ዐይኑን ከማሸሹ በፊት የምታውቀው ወንድ መሆኑን ለይታ ጥርሷን ብልጭ አረገችለት እሷን ፍለጋ ያልመጣ ለመምሰል እጁን ኪሱ ከትቶ በግዴለሽ አረማመድ ተጠጋት ስሜቱን ለመሸፈን በከንቱ ደከመ እንጂ በድንጋጤ ፊቱ ቀልቶ ግንባሩን አልቦት ነበር።

ውይ ! አንተ ነህ እንዴ ? በሞትኩት ! ምነው ጠፋህ ? ” አለች ከልብ በሆነ አነጋግር ።

ምንም ሳይመልስላት ስሜቱን በፈግግታ ብልጭታ ለመሸፈን እየሞከረ ጨበጣት

ሙት እውነቴን እኮ ነው ጠፋህ ? ቆይ እስኪ ስንት ቀን ሆነን አዎ ሳምንት አልፎሃል ። እኔ ከዛሬ ነገ ትመጣለህህ እያልኩ በልቤ ሳስብህ ነበር አለችው።

“ እነቷን ይሆን እንዴ ? ” ሲል አሰበ ግን አሁንም ከመቅለስለስና ራሰን ከማከክ ሌላ ምንም አልመለሰም ። ድምጿ የእውነት ቅላጼ ነበረው የተናገረችው የልቧን ነው ፤ ለአቤል አንድ ጥሩ የሆነ ስሜት አድሮበታል ። ሴት ያልለመደ መሆኑና የተማረ መሆኑ ፥ በስሜቷ ውስጥ እንዲቀረጽ አድርጎታል እናም እንዳለችው አብራው ካደረችበት ሌሊት በኋላ ዐልፎ ዐልፎ በልቧ ታስበው ነበር ። የተሰማራችበት ሙያ ሆነና በወሲብ ተገናኙ እንጂ ፥ እሷ ለሱ ያደረባት ስሜት ሐሳቧንና ችግሯን እንደምታዋየው
እሱም በዕውቀቱ እንደሚረዳት የቅርብ ዘመዷ ወይም ታናሽ ወንድሟ ዐይነት ነበር

“ በል እሺ ግባ ! በር ላይ አትቁም አለችው ከእሱ አንዳችም ቃል ባለመስማቷ እያዘነች ።

“አአይ ልሒድ ፤ድንገት ሳልፍ'ኮ ነው
👍2