#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
በገለጻው አዳራሽ የተሰበሰቡት ተማሪዎች ከትከት ብለው ሣቁ ። አቤል ግን ሌክቸረሩ የተናገረውን ቀልድ ስላላዳመጠ ለመሣቅ ዕድል አላጋጠመውም ። በአዳራሹ ሣቅ
ተኮርኩሮ ከሐሳቡ ከነቃ በኋላ አጠገቡ የነበረውን ተማሪ ስለ ሁኔታው እንዲያስረዳው ጠየቀው ።
ምንድነው? አለወ ድንግርግር ባለ ስሜት
አልሰማኸውም እንዴ ? ” ብሎ ተማሪው ቀልዱን ሊነግረው ሲሞክርም ሣቁን መግታት አልቻለም ነበር ።አቤል ደግሞ የተማሪውን ሣቅ አስጨርሶ ቀልዱን ለማዳመጥ ትዕግሥት አልነበረውም ። በተሰላቸ ስሜት ቸልብሎ ተወው ።
ሰኞን አይወደውም ብላክ መንዴይ ይለዋል ።ቅዳሜና እሑድን መንፈሱንም ባይሆን አካሉን አሳርፎ ሰኞ ደብተሩን ይዞ ወደ ትምህርት ክፍል ሲገባ አንዳች የጥላቻ ስሜት ያድርበታል ። እንዲያው ለስሜቱ ይቅርታ ለመስጠት ያህል ቀናቱን በመውደድና ባለመውደድ ይከፋፍላቸዋል
እንጂ ፥ ልቡ ውስጥ ለትዕግሥት ቦታ ከሰጣት ጊዜ ጀምሮ የመምህሮቹን ገለጻ በሙሉ ስሜት ያዳመጠበት ጊዜ የለም ።
ሐሳቡ ውጭ እየከነፈበት አካሉ ብቻ ነበር ክፍሉ ውስጥ የሚቀመጠው ።
ከሌሎቹ ሁሉ ይህን ክፍለ ጊዜ ይወደው ነበር ።የፍልስፍና ተማሪዎቹ ሳይወስዱ ያለፉትን አንድ የሳይኮሎጂ ኮርስ ከሁለተኛ ዓመት ተማሪዎች ጋር የሚወስዱበት ክፍለ ጊዜ በመሆኑ ፥ ከትምህርቱ ይልቅ አዳራሹ ሞልቶ ማየቱ ያስደስተዋል ። ምክንያቱም ሌሎቹን ኮርሶች የሚወስደው ከስድስቱ ተማሪዎች ጋር ብቻ ነው ። በቁጥር ማነሳቸው ደግሞ
መምህሩ የተማሪዎቹን ስሜትና ሁኔታ በቀላሉ እንዲከታተል ይረዳዋል ። በዚያ ላይ ጥያቄ መጠየቅ አለ ።አቤል ይህን ነው ያልወደደው ፤ አካሉን ክፍል ውስጥ አሰቀምጦ በሰሜቱ ወደ ወጭ የመብረሩን ነጻነት ያሳፈዋል ፤ በቀላሉ
ይጋለጣል ።
ዛሬ ግን ሰኞ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ሌላም ስሜትን ያቁነጠነጠው ጉዳይ ነበር ። ትዕግሥትን ማየት አለበት ። የሁለት
ቀን ናፍቆት ላለበት አፍቃሪ የአንድ ሰዓት ሌክቸር በጣም ረጅም ነው ። እናም ከክፍሉ ሮጦ ለመውጣት የደወሏን
ድምፅ ነበር የሚጠባበቀው ።
ምን መስለህ ? አለው አጠገቡ የተቀመጠ ተማሪ ሣቁን እንደጨረሰ
የመምህሩን ቀልድ ለአቤል ለመንገር
ጓጉቶ ሃይማኖታዊ ቀልድ ነውኮ የተናገረው ።
እኮ ምን አለ አቤል በተሰላቸ ድምፅ ።
“ ሰዎቹ ከሞቱ በኋላ ወደ ሰማይ ቤት ሔደው መንግስት ሰማያት ለመግባት ሽሚያ ተፈጠረ ። የገነት በር ጠባብ ነበር ስለዚህ ጻድቃኖቹ ተወዳድረወ ይግቡ
ተባለና መመዘኛው በምድር ላይ ለደሃ የመጸወቱት ገንዘብ ብዛት ሆነ ። በዚህም መሠረት ለደሃ ብዙ የመጸወቱት ወደ
ገነት ሲገቡ አምስት ሳንቲም ብቻ የመጸወጡት ጻድቅ ግን አምስት ሳንቲሙ ተመልሶለት ወደ ገሀነም ይግባ ተባለ።
አቤል ቀልዱ ብዙም ስላልኮረኮረው ፥ ጥርሱን ትንሽ ብልጭ አድርጎ ሰዓትህ ስንት ትላለች ? መውጫችን አልደረሰም
እንዴ? ሲል ጠየቀው ።
ተማሪው ሰዓቱን ተመልክቶ፡ “ ሁለት ደቂቃ ይቀራል” አለው።
ሁለት ዓመት ይቀራል ያለው ይመስል አቤል ፊቱን ኮሶ አስመስሎ በልቡ ሴኮንዶቹን ሲያባርር ቆየ ።
ልክ የደወሏን ድምፅ ሲሰማ አንዳች ነገር መቀመጫውን እንደ ወጋው ሁሉ ቶሎ ብድግ አለ ። ነገር ግን አልተትኮረበትም ። ሌሎቹም ለመመገቢያ አዳራሹ ሰልፍ ለመሽቀዳደም ደውሉን ተከትለው ግልብጥ ብለው ስለተነሱ ክፍሉ ትርምሱ ወጣ ። ቀድሞ ለመውጣት በሩ ላይ ጭንቅንቅ ተፈጠረ
ምናለበት ቅድሚያ ቢሰጡኝ ? አለ አቤል በልቡ ለመውጣት እየተጋፋ “ እነሱ የራባቸው ሆዳቸውን ነው»የእኔው ግን የዐይን ረሀብ ነው ።
“ ታዲያ ከዐይን ረሀብና ከሆድ ረሀብ ለየትኛው ነው ቅድሚያ የሚሰጠው ? ” ሲል የገዛ ኅሊናው ያፋጠጠው
መሰለው።
እንደ ረሀቡ ጥንካሬ መሰለኝ ። ”
አይደለም ። ጅል አትሁን ። ሆድህ ሳይጠግብ ዐይንህ አይራብም ።
አረ አይመስለኝም ። አያድርስ ነው ። የዐይን ረሀብ ራሱ ከሆድ ረሀብ ይብሳል አያድርስ ነው ! እረ እንዲያው መቃጠል ነው !?
“ ምነው የዐይንን ረሀብ እንዲህ አጋነንከው ? የማያውቁት ዐይነ ሥውራን አሉ አይደለም እንዴ ? ”
“ ሀሀ ! እነሱም ” ኮ ጆሮአቸው የሚራብ ይመስለኛል ። ጆሮአቸው የዐይናቸውን ያህል ያገለግላቸዋል ። ለምሳሌ እኛ ዐይናማዎቹ የምንወዳትን ሴት በየጊዚው ለማየት እንደምንራበው ሁሉ ፡ እነሱም የሚወዷትን ሴት ኮቴ ወይም ድምፅ ለመስማት ጆሮአቸው የሚራብ ይመስለኛል ። ”
• ድንቅ የሆነ የመከላከያ ሐተታ ነው ። እስቲ እንግዲህ አንድ ሁለት ቀን ምግብ ሳትበላ ቆይና ፥ ከዐይንህና ከሆድህ
የትኛው ቅድሚያ እንደሚኖረው ትረዳዋለህ ። ”
አቤል ወትዋች ኅሊናውን “ ወጊድልኝ!” ብሎ የማማረር ያህል እጁን አወራጭቶ ፥ “ ሰው ኅሊናን ያህል ባላንጣ።ባይኖረው ምንኛ እንደ ልቡ በሆነ ነበር ! ” ሲል አሰበ
“ እንዴት እባክህ ? እንደ ከብት ? እንደ እንስሳ? ”እያለ ኅሊናው እንደገና ከተፍ ።
መንገዱን በምን ዐይነት ርምጃ እንደ ጨረሰው ለራሱ” እየገረመው ከመኝታ ክፍሉ ደረሰ ። ደብተሩን እልጋው ላይ ወረወረና በወጣበት ፍጥነት ተመልሶ ደረጃውን ወረደ በሩጫ ቀረሽ ርምጃ ወደ ምግብ አዳራሽ አመራ ከገለጻ ክፍሉ ለመውጣት የነበረው ችኮላ " ያ ሁሉ የዐይን ረሃብሬ የተመረኮዘ ግላዊ ሙግት ፥ ይህ ሁሉ ሩጫ ትዕግሥትን ለማየት ነው ። ትላንት ጠዋት ወደ ሰርጉ ከሔደችበት ጊዜ ጀምሮ አላያትም ። እሔደችበት አድራለች ብሎ ነው የገመተው ። እሷ ግን አውቶቡስ አጥታ አምሽታ ነበር እንጂ ካምፓስ ነው ያደረችው ። ጠዋት ደግሞ እሱ ራሱ እንቅልፍ ተጫጭኖት ስላረፈደ እንደ ወትሮው ወደ ቁርስ ክፍል ስትሔድ ወይም ወደ ትምህርት ክፍሏ ስትገባ ለማየት ዕድል አልገጠመውም ። በዚህ ምክንያት ገለጻ ክፍሉ ውስጥ ሁሉ
ነገሩን እያብላላ ሲበሽቅ ነው ያረፈደው ።
አሁንም ከምግብ አዳራሹ አካባቢ ደርሶ የምሳ ሰልፍ እንደ ያዘ ። መላ ሰውነቱ በቅናትና በእልህ ነበልባል ይንቀለቀል ነበር ። ትዕግሥት ሰልፉ ውስጥ የለችም ቀድማ ገብታ ይሆን ? ሰልፍ መጠበቁ አስመረረው ። ወደ ውስጥ ለመግባት
ቸኰል ። ነገር ግን ተራ መጠበቅ ግዴታ ነው ። በውዴታ ግዴታ የተሳሰረች ዓለም !
ተራው ደርሶ ውስጥ ከገባ በኋላ ፡ እንጀራ ሳይቀበል ወጥ ጨላፊዋ ጋ ሔዶ ትሪውን ዘረጋለት ። መሳሳቱን ያወቀው ሲሥቅበት ነው ። ድርሻውን ተቀብሎ መቀመጫ
በሚፈልግበት ጊዜም ዐይኑ አዳራሹን ዙሪያ ገብ እየማተረ ነበር ። በተለይ ሴቶች ፀየተቀመጡበትን አካባቢ እሳት
በጎረሱ ዐይኖቹ ቃኘ ።
ዛሬም አልመጣችም ማለት ነው ? ” አለ በልቡ ሳያስበው ጥርሶቹን እያንቀጫቀጨ ከኅሊናው ጋር እንደ ልቡ ለመሟገት ተናግሮ ከሚያናግር ለመሸሽ ፥ ከታዛቢ ለመራቅና ግላዊ ነጻነቱን ለማግኘት አብዛኛውን ጊዜ በምግብ አዳራሹ ውስጥ ብቻውን ተቀምጦ
መብላት ይመርጣል ። ሰላምን ከብቸኝነት ሊያገኛት ይጥራል ። ይህ ዐይን ፍቅር ላይ ከመውደቁ በፊትም የነበረው ጸባይ ነው ። በእርግጥ ፥ በዐይን ፍቅሩ ሳቢያ ደረጃው ከፍ ብሏል ። አሁንም ከወደ ጥግ በኩል ባዶ ጠረጴዛ ተመልክቶ
ወደዚያው ሲያመራ ትዕግሥት ተመለከተችው ። የጎረሰችው አፏ ውስጥ ተንቀዋለለባት ። ቶሎ ብላ ዐይኗን ልትሰ
ብር ስትል ማርታ ቀለበቻት ። ቤተልሔም ሁለተኛዉ ምግብ አዳራሽ ስለምትመገብ አብራቸው አልነበረችም ።
“ ኤጭ ! እንዲያው ይሄ የማሽላ እንጀራቸው!” አለች ማርታ ትዕግሥትን ላለማሳፈር ብላ ። በእርግጥም የእሑዱ
ግብዣ ገና ከውስጧ ስላልጠፋ ፡ ሽሮው አልዋጥ ብሏት እየታገለች ነበር ።
ትዕግሥት ምንም አላለችም ። ከዚያ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
በገለጻው አዳራሽ የተሰበሰቡት ተማሪዎች ከትከት ብለው ሣቁ ። አቤል ግን ሌክቸረሩ የተናገረውን ቀልድ ስላላዳመጠ ለመሣቅ ዕድል አላጋጠመውም ። በአዳራሹ ሣቅ
ተኮርኩሮ ከሐሳቡ ከነቃ በኋላ አጠገቡ የነበረውን ተማሪ ስለ ሁኔታው እንዲያስረዳው ጠየቀው ።
ምንድነው? አለወ ድንግርግር ባለ ስሜት
አልሰማኸውም እንዴ ? ” ብሎ ተማሪው ቀልዱን ሊነግረው ሲሞክርም ሣቁን መግታት አልቻለም ነበር ።አቤል ደግሞ የተማሪውን ሣቅ አስጨርሶ ቀልዱን ለማዳመጥ ትዕግሥት አልነበረውም ። በተሰላቸ ስሜት ቸልብሎ ተወው ።
ሰኞን አይወደውም ብላክ መንዴይ ይለዋል ።ቅዳሜና እሑድን መንፈሱንም ባይሆን አካሉን አሳርፎ ሰኞ ደብተሩን ይዞ ወደ ትምህርት ክፍል ሲገባ አንዳች የጥላቻ ስሜት ያድርበታል ። እንዲያው ለስሜቱ ይቅርታ ለመስጠት ያህል ቀናቱን በመውደድና ባለመውደድ ይከፋፍላቸዋል
እንጂ ፥ ልቡ ውስጥ ለትዕግሥት ቦታ ከሰጣት ጊዜ ጀምሮ የመምህሮቹን ገለጻ በሙሉ ስሜት ያዳመጠበት ጊዜ የለም ።
ሐሳቡ ውጭ እየከነፈበት አካሉ ብቻ ነበር ክፍሉ ውስጥ የሚቀመጠው ።
ከሌሎቹ ሁሉ ይህን ክፍለ ጊዜ ይወደው ነበር ።የፍልስፍና ተማሪዎቹ ሳይወስዱ ያለፉትን አንድ የሳይኮሎጂ ኮርስ ከሁለተኛ ዓመት ተማሪዎች ጋር የሚወስዱበት ክፍለ ጊዜ በመሆኑ ፥ ከትምህርቱ ይልቅ አዳራሹ ሞልቶ ማየቱ ያስደስተዋል ። ምክንያቱም ሌሎቹን ኮርሶች የሚወስደው ከስድስቱ ተማሪዎች ጋር ብቻ ነው ። በቁጥር ማነሳቸው ደግሞ
መምህሩ የተማሪዎቹን ስሜትና ሁኔታ በቀላሉ እንዲከታተል ይረዳዋል ። በዚያ ላይ ጥያቄ መጠየቅ አለ ።አቤል ይህን ነው ያልወደደው ፤ አካሉን ክፍል ውስጥ አሰቀምጦ በሰሜቱ ወደ ወጭ የመብረሩን ነጻነት ያሳፈዋል ፤ በቀላሉ
ይጋለጣል ።
ዛሬ ግን ሰኞ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ሌላም ስሜትን ያቁነጠነጠው ጉዳይ ነበር ። ትዕግሥትን ማየት አለበት ። የሁለት
ቀን ናፍቆት ላለበት አፍቃሪ የአንድ ሰዓት ሌክቸር በጣም ረጅም ነው ። እናም ከክፍሉ ሮጦ ለመውጣት የደወሏን
ድምፅ ነበር የሚጠባበቀው ።
ምን መስለህ ? አለው አጠገቡ የተቀመጠ ተማሪ ሣቁን እንደጨረሰ
የመምህሩን ቀልድ ለአቤል ለመንገር
ጓጉቶ ሃይማኖታዊ ቀልድ ነውኮ የተናገረው ።
እኮ ምን አለ አቤል በተሰላቸ ድምፅ ።
“ ሰዎቹ ከሞቱ በኋላ ወደ ሰማይ ቤት ሔደው መንግስት ሰማያት ለመግባት ሽሚያ ተፈጠረ ። የገነት በር ጠባብ ነበር ስለዚህ ጻድቃኖቹ ተወዳድረወ ይግቡ
ተባለና መመዘኛው በምድር ላይ ለደሃ የመጸወቱት ገንዘብ ብዛት ሆነ ። በዚህም መሠረት ለደሃ ብዙ የመጸወቱት ወደ
ገነት ሲገቡ አምስት ሳንቲም ብቻ የመጸወጡት ጻድቅ ግን አምስት ሳንቲሙ ተመልሶለት ወደ ገሀነም ይግባ ተባለ።
አቤል ቀልዱ ብዙም ስላልኮረኮረው ፥ ጥርሱን ትንሽ ብልጭ አድርጎ ሰዓትህ ስንት ትላለች ? መውጫችን አልደረሰም
እንዴ? ሲል ጠየቀው ።
ተማሪው ሰዓቱን ተመልክቶ፡ “ ሁለት ደቂቃ ይቀራል” አለው።
ሁለት ዓመት ይቀራል ያለው ይመስል አቤል ፊቱን ኮሶ አስመስሎ በልቡ ሴኮንዶቹን ሲያባርር ቆየ ።
ልክ የደወሏን ድምፅ ሲሰማ አንዳች ነገር መቀመጫውን እንደ ወጋው ሁሉ ቶሎ ብድግ አለ ። ነገር ግን አልተትኮረበትም ። ሌሎቹም ለመመገቢያ አዳራሹ ሰልፍ ለመሽቀዳደም ደውሉን ተከትለው ግልብጥ ብለው ስለተነሱ ክፍሉ ትርምሱ ወጣ ። ቀድሞ ለመውጣት በሩ ላይ ጭንቅንቅ ተፈጠረ
ምናለበት ቅድሚያ ቢሰጡኝ ? አለ አቤል በልቡ ለመውጣት እየተጋፋ “ እነሱ የራባቸው ሆዳቸውን ነው»የእኔው ግን የዐይን ረሀብ ነው ።
“ ታዲያ ከዐይን ረሀብና ከሆድ ረሀብ ለየትኛው ነው ቅድሚያ የሚሰጠው ? ” ሲል የገዛ ኅሊናው ያፋጠጠው
መሰለው።
እንደ ረሀቡ ጥንካሬ መሰለኝ ። ”
አይደለም ። ጅል አትሁን ። ሆድህ ሳይጠግብ ዐይንህ አይራብም ።
አረ አይመስለኝም ። አያድርስ ነው ። የዐይን ረሀብ ራሱ ከሆድ ረሀብ ይብሳል አያድርስ ነው ! እረ እንዲያው መቃጠል ነው !?
“ ምነው የዐይንን ረሀብ እንዲህ አጋነንከው ? የማያውቁት ዐይነ ሥውራን አሉ አይደለም እንዴ ? ”
“ ሀሀ ! እነሱም ” ኮ ጆሮአቸው የሚራብ ይመስለኛል ። ጆሮአቸው የዐይናቸውን ያህል ያገለግላቸዋል ። ለምሳሌ እኛ ዐይናማዎቹ የምንወዳትን ሴት በየጊዚው ለማየት እንደምንራበው ሁሉ ፡ እነሱም የሚወዷትን ሴት ኮቴ ወይም ድምፅ ለመስማት ጆሮአቸው የሚራብ ይመስለኛል ። ”
• ድንቅ የሆነ የመከላከያ ሐተታ ነው ። እስቲ እንግዲህ አንድ ሁለት ቀን ምግብ ሳትበላ ቆይና ፥ ከዐይንህና ከሆድህ
የትኛው ቅድሚያ እንደሚኖረው ትረዳዋለህ ። ”
አቤል ወትዋች ኅሊናውን “ ወጊድልኝ!” ብሎ የማማረር ያህል እጁን አወራጭቶ ፥ “ ሰው ኅሊናን ያህል ባላንጣ።ባይኖረው ምንኛ እንደ ልቡ በሆነ ነበር ! ” ሲል አሰበ
“ እንዴት እባክህ ? እንደ ከብት ? እንደ እንስሳ? ”እያለ ኅሊናው እንደገና ከተፍ ።
መንገዱን በምን ዐይነት ርምጃ እንደ ጨረሰው ለራሱ” እየገረመው ከመኝታ ክፍሉ ደረሰ ። ደብተሩን እልጋው ላይ ወረወረና በወጣበት ፍጥነት ተመልሶ ደረጃውን ወረደ በሩጫ ቀረሽ ርምጃ ወደ ምግብ አዳራሽ አመራ ከገለጻ ክፍሉ ለመውጣት የነበረው ችኮላ " ያ ሁሉ የዐይን ረሃብሬ የተመረኮዘ ግላዊ ሙግት ፥ ይህ ሁሉ ሩጫ ትዕግሥትን ለማየት ነው ። ትላንት ጠዋት ወደ ሰርጉ ከሔደችበት ጊዜ ጀምሮ አላያትም ። እሔደችበት አድራለች ብሎ ነው የገመተው ። እሷ ግን አውቶቡስ አጥታ አምሽታ ነበር እንጂ ካምፓስ ነው ያደረችው ። ጠዋት ደግሞ እሱ ራሱ እንቅልፍ ተጫጭኖት ስላረፈደ እንደ ወትሮው ወደ ቁርስ ክፍል ስትሔድ ወይም ወደ ትምህርት ክፍሏ ስትገባ ለማየት ዕድል አልገጠመውም ። በዚህ ምክንያት ገለጻ ክፍሉ ውስጥ ሁሉ
ነገሩን እያብላላ ሲበሽቅ ነው ያረፈደው ።
አሁንም ከምግብ አዳራሹ አካባቢ ደርሶ የምሳ ሰልፍ እንደ ያዘ ። መላ ሰውነቱ በቅናትና በእልህ ነበልባል ይንቀለቀል ነበር ። ትዕግሥት ሰልፉ ውስጥ የለችም ቀድማ ገብታ ይሆን ? ሰልፍ መጠበቁ አስመረረው ። ወደ ውስጥ ለመግባት
ቸኰል ። ነገር ግን ተራ መጠበቅ ግዴታ ነው ። በውዴታ ግዴታ የተሳሰረች ዓለም !
ተራው ደርሶ ውስጥ ከገባ በኋላ ፡ እንጀራ ሳይቀበል ወጥ ጨላፊዋ ጋ ሔዶ ትሪውን ዘረጋለት ። መሳሳቱን ያወቀው ሲሥቅበት ነው ። ድርሻውን ተቀብሎ መቀመጫ
በሚፈልግበት ጊዜም ዐይኑ አዳራሹን ዙሪያ ገብ እየማተረ ነበር ። በተለይ ሴቶች ፀየተቀመጡበትን አካባቢ እሳት
በጎረሱ ዐይኖቹ ቃኘ ።
ዛሬም አልመጣችም ማለት ነው ? ” አለ በልቡ ሳያስበው ጥርሶቹን እያንቀጫቀጨ ከኅሊናው ጋር እንደ ልቡ ለመሟገት ተናግሮ ከሚያናግር ለመሸሽ ፥ ከታዛቢ ለመራቅና ግላዊ ነጻነቱን ለማግኘት አብዛኛውን ጊዜ በምግብ አዳራሹ ውስጥ ብቻውን ተቀምጦ
መብላት ይመርጣል ። ሰላምን ከብቸኝነት ሊያገኛት ይጥራል ። ይህ ዐይን ፍቅር ላይ ከመውደቁ በፊትም የነበረው ጸባይ ነው ። በእርግጥ ፥ በዐይን ፍቅሩ ሳቢያ ደረጃው ከፍ ብሏል ። አሁንም ከወደ ጥግ በኩል ባዶ ጠረጴዛ ተመልክቶ
ወደዚያው ሲያመራ ትዕግሥት ተመለከተችው ። የጎረሰችው አፏ ውስጥ ተንቀዋለለባት ። ቶሎ ብላ ዐይኗን ልትሰ
ብር ስትል ማርታ ቀለበቻት ። ቤተልሔም ሁለተኛዉ ምግብ አዳራሽ ስለምትመገብ አብራቸው አልነበረችም ።
“ ኤጭ ! እንዲያው ይሄ የማሽላ እንጀራቸው!” አለች ማርታ ትዕግሥትን ላለማሳፈር ብላ ። በእርግጥም የእሑዱ
ግብዣ ገና ከውስጧ ስላልጠፋ ፡ ሽሮው አልዋጥ ብሏት እየታገለች ነበር ።
ትዕግሥት ምንም አላለችም ። ከዚያ
👍1
በኋላ ቀናም አላለች ።
አቤል መቀመጥ የፈለገበት አካባቢ ሲደርስ ድንገት አየችው ። የቅናት እሳት የሚተፉት ዐይኖቹ በድንገትኛው
አይታ ከማርታ ጋር በመገጣጠማቸው ድንግጥግጥ አለ ።እግሩ የተሳሰረ መሰለው ። ዐይኑን ሳይሰብር ከድንጋጤው ለማምለጥ ራመድ ሲል የአንዱ ወንበር እግር ጠለፈው ።
በሁለት እጁ የምግብ ትሪውን ይዞ ስለ ነበር ተንገዳግዶ ሚዛኑን ጠብቆ መዳን አልቻለም። አሳዛኝትርኢት ሆነ። እሱ
ከታች ፡ ያድነኛል ብሎ የተደገፈው ወንበር እግሩ ላይ ሲወ ድቅ የትሪው እንጀራና ወጥ ተገልብጦ ደረቱ ላይ ተደፋ ።
የትኩሱ ወጥ ፍንጣቂ የደረሰባቸው በአካባቢው የተቀመጡ ተማሪዎች ተቆጥተው እየተፈናጠሩ ቢነሡም ትርኢቱ
ቁጣቸውን ወደ ሣቅ ለወጠው ። ካካታውን ሰምቶ የአዳራሹ ተመጋቢ ሁሉግልብጥብሎ ተነሣ በአንዱ ውድቀት ሌላዉ ሊሥቅ ፡ የሳምንቱ መሣቂያና መሳሳቂያ ሆኖ የሚቆየው ወሬ ከሌላ አፍ ከመስማት ይልቅ በዐይኑ በብሌኑ ለማየት
አንዱ ባንዱ ላይ መንጠራራት ራሱ ሌላ ትርኢት ሆነ ።
እስክንድርም እንደ ሌሎቹ ተንጠራርቶ ሲያይ ተዋናዩ አቤል መሆኑን በተመለከተ ጊዜ ዐይኑን ማመን አቃተው ።ግፊያውን እየበረጋገደ ዐልፎ አጠገቡ ሲደርስ • በወጥ የተጨማለቀ ልብሱን እየጠራረገለት “ አቤል” አቤል ነው ?
ምን ነካህ ? ” አለው ።
አቤል ምንም አልመለሰለትም « ከወደቀበት ተነሥቶ ቢቆምም በድንጋጤ ክው ብሎአል ። ከዚያ አዳራሽ ተፈት
ልኮ መውጣት ነበር ፍላጎቱ ። ግን በየት በኩል? የዚያ ሁሉ ተማሪ ዐይን አንድ ርምጃም እንደማያራምደው ገመተ ።
ሆኖም እስክንድርን አጠገቡ በማግኘቱ ትንሽ ቀለል አለው ።
ትንግሥት በዚች ደቂቃ ውስጥ መሬት ቁልቁል ተሰንጥቃ ብትውጣት ምንኛ በወደደች ! ካካታውን ሰምታ ቀና
ስትልና አቤል ከያዘው ትሪ ጋር ሲወድቅ ስትመለከት ፡ ሽምቅቅ ብላ አንገቷን ጠረጴዛው ላይ እንደ ደፋች ቀረች ። የሚ
ቀጥለውን ትርኢትም ለማየት ቀና አላለችም ። ተማሪው ሁሉ ወደ ወደቀው ወጣት ሳይሆን ወደ እሷ የሚያይ መሰላት
እንባዋ ድንገት ሊመጣባት ሲል ገታችው
አቤል በምግብ አዳራሹ በር ከእስክንድር ጋር ሲወጣ ማርታ ተመለከተች ። እሷም በድንጋጤ የምትገባበት ጠፍቷታል ። ተደናግጦ ለመውደቁ ምክንያት የሆነው ከእሷ ጋር ዐይን ዐይን መገጣጠማቸው ስለ መሰላት ፥ የኃጢአተኝነት ስሜት ተሰምቷታል ።
ት... ትዕግሥት ” አለቻት ፈራ ተባ በሚል
ድምፅ።
ወዬ ! ”
እንሒድ ፥ እን ውጣ ትዕግሥት እንባዋ እንዳይመጣ እንደ ምንም እየተጠነ
ቀቀች ቀስ ብላ ቀና አለች ። እንደ ፈራችው አልሆነም እዳራሹ ውስጥ ያሉት ተማሪዎች በሁኔታው እየሳቁ ምግባቸውን ከማጣጣም በስተቀር እነትዕግሥትን ልብ ብለው አልተመለከቷቸውም ።
የበሉ!ትን ትሪ ሳያነሱ ፥ ግራ ቀኝ ሳይመለከቱ ሁለቱም አንገታቸውን እቅርቅረው ፈትለክ ብለው ወጡ ።
ከቀትር በኋላ ወደ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ ፥ እስክንድር ከመኝታ ክፍሉ ተጠራ ። አልጋው ላይ ጋደም ብሎ እያነበቀ
ነበር።
ማን ነው የፈለገኝ ? አለው : ተልኮ የመጣውን አንዲት ልጅ ናት ። ወደዚህ ስመጣ አይታኝ አንተን እንድጠራላት ጠየቀችኝ ።
“ ስሜን የምታውቅ ናት ? ”
“ እሷ፡ ስምህን ጠርታ ነው ንገርልኝ ያለችኝ
በፈጣን ርምጃ ከመኝታ ክፍሉ ወጥቶ ፥ ደረጃውን ወርዶ ወደ ውጪ ብቅ ሲል ማርታ ደመቀን ቆማ ተመለከታት »
ግር አለው ። ከአሁን በፊት ግቢው ውስጥ መታየት ካልሆነ በስተቀር ንግግር አልነበራቸውም።
ማርታ እሷ እንዳስጠራችው እንዲያውቅ ፈገግ አለችለት ። ዝብርቅርቅ ባለ ስሜት ልቡ እየነጠረ ቀረባት ።
እኔ ጋ ነው ? ” አላት የውስጥ ስሜቱን በሚገልጽ ጣፋጭ ቅላጼ ።
“አዎ! ስለ አቤል ልጠይቅህ ነው ” አለችው ዕዝን ብላ።
የአቤልንም የእኔንም ስም እንዴት አወቀች ? ” ሲል አሰበ ። ወዲያው ግን ለምን ጅል እሆናለሁ ? እኔ እራሴ
የእሷንና የትዕግሥትን ስም አጣርቼ ዐውቅ የለም እንዴ ! የእነሱ ማወቅ ያስደንቃል ? እንዲያውም ለወሬ ሴቶች ይብሳሉ ” አለ ፡ ባይነጋገሩም በዐይን እየተራረፉ የተላለፉበትን ቀን በልቡ እያስታወሰ ።
እንደ ሴትነቷ ስማቸውን ዐውቃ እንዳላወቀች ለመሆን አለመሞከሯ አስደነቀው ። አመጣጧ ብዙ ነገር ጭንቅላቱ ውስጥ አተረማመሰበት ። የተጠቀለለ ነገር ይዛለች ።
ትዕግሥት ራሷ መምጣት ፈርታ ልካት ይሆን?” ሲል አሰበ ። በምግብ አዳራሽ ውስጥ ለአቤል መውደቅ መንስኤው
ከእነሱ ጋር እንደ ተያያዜ ፈጽሞ አላወቀም ነበር ።
ምግብ ቤት ውስጥ ሲወድቅ ነበርሽ እንዴ ? ” አላትና ፥ ከእሷ መልስ ሳይጠብቅ ። የትኩሱ ወጥ ፍንጣቂ
እጁን ትንሽ ጠበሰው እንጂ ሌላ ቦታ አልተጎዳም ” አላት ።
ከንፈሯን መጠጠች
“ እምልሽ ፡ መቼም እዚያ ሁሉ ተማሪ መሐል መውደቁ ራሱ ሕመም ነው ። አለ አይደል ! የአጋጣሚ ነገር ቢሆንም ያሳፍራል ። እና በድንጋጤ ትንሽ ተረብሾ ፡ ምሳውንም ባመጣለት ሊበላ ኣልቻለም ። አሁን ተኝቷል ። ድንጋጤው ሲያልፍለትና ሁኔታው ሲረሳው ደኅና ይሆናል አላት »
እንደ ገና ከንፈሯን መጠጠችና “ ውይ በናትህ 'አወዳደቁ እንዴት ሰቀጠቅጠኝ መሰለህ ! ብቻ እንኳን ተረፈ አለችው ።
አስተዛዘኗ ልቡን ነካው ። ምነው እኔ በወደቅኩና እንዲህ ባዘንሽልኝ ! ” አለ በሐሳቡ ።
💥ይቀጥላል💥
አቤል መቀመጥ የፈለገበት አካባቢ ሲደርስ ድንገት አየችው ። የቅናት እሳት የሚተፉት ዐይኖቹ በድንገትኛው
አይታ ከማርታ ጋር በመገጣጠማቸው ድንግጥግጥ አለ ።እግሩ የተሳሰረ መሰለው ። ዐይኑን ሳይሰብር ከድንጋጤው ለማምለጥ ራመድ ሲል የአንዱ ወንበር እግር ጠለፈው ።
በሁለት እጁ የምግብ ትሪውን ይዞ ስለ ነበር ተንገዳግዶ ሚዛኑን ጠብቆ መዳን አልቻለም። አሳዛኝትርኢት ሆነ። እሱ
ከታች ፡ ያድነኛል ብሎ የተደገፈው ወንበር እግሩ ላይ ሲወ ድቅ የትሪው እንጀራና ወጥ ተገልብጦ ደረቱ ላይ ተደፋ ።
የትኩሱ ወጥ ፍንጣቂ የደረሰባቸው በአካባቢው የተቀመጡ ተማሪዎች ተቆጥተው እየተፈናጠሩ ቢነሡም ትርኢቱ
ቁጣቸውን ወደ ሣቅ ለወጠው ። ካካታውን ሰምቶ የአዳራሹ ተመጋቢ ሁሉግልብጥብሎ ተነሣ በአንዱ ውድቀት ሌላዉ ሊሥቅ ፡ የሳምንቱ መሣቂያና መሳሳቂያ ሆኖ የሚቆየው ወሬ ከሌላ አፍ ከመስማት ይልቅ በዐይኑ በብሌኑ ለማየት
አንዱ ባንዱ ላይ መንጠራራት ራሱ ሌላ ትርኢት ሆነ ።
እስክንድርም እንደ ሌሎቹ ተንጠራርቶ ሲያይ ተዋናዩ አቤል መሆኑን በተመለከተ ጊዜ ዐይኑን ማመን አቃተው ።ግፊያውን እየበረጋገደ ዐልፎ አጠገቡ ሲደርስ • በወጥ የተጨማለቀ ልብሱን እየጠራረገለት “ አቤል” አቤል ነው ?
ምን ነካህ ? ” አለው ።
አቤል ምንም አልመለሰለትም « ከወደቀበት ተነሥቶ ቢቆምም በድንጋጤ ክው ብሎአል ። ከዚያ አዳራሽ ተፈት
ልኮ መውጣት ነበር ፍላጎቱ ። ግን በየት በኩል? የዚያ ሁሉ ተማሪ ዐይን አንድ ርምጃም እንደማያራምደው ገመተ ።
ሆኖም እስክንድርን አጠገቡ በማግኘቱ ትንሽ ቀለል አለው ።
ትንግሥት በዚች ደቂቃ ውስጥ መሬት ቁልቁል ተሰንጥቃ ብትውጣት ምንኛ በወደደች ! ካካታውን ሰምታ ቀና
ስትልና አቤል ከያዘው ትሪ ጋር ሲወድቅ ስትመለከት ፡ ሽምቅቅ ብላ አንገቷን ጠረጴዛው ላይ እንደ ደፋች ቀረች ። የሚ
ቀጥለውን ትርኢትም ለማየት ቀና አላለችም ። ተማሪው ሁሉ ወደ ወደቀው ወጣት ሳይሆን ወደ እሷ የሚያይ መሰላት
እንባዋ ድንገት ሊመጣባት ሲል ገታችው
አቤል በምግብ አዳራሹ በር ከእስክንድር ጋር ሲወጣ ማርታ ተመለከተች ። እሷም በድንጋጤ የምትገባበት ጠፍቷታል ። ተደናግጦ ለመውደቁ ምክንያት የሆነው ከእሷ ጋር ዐይን ዐይን መገጣጠማቸው ስለ መሰላት ፥ የኃጢአተኝነት ስሜት ተሰምቷታል ።
ት... ትዕግሥት ” አለቻት ፈራ ተባ በሚል
ድምፅ።
ወዬ ! ”
እንሒድ ፥ እን ውጣ ትዕግሥት እንባዋ እንዳይመጣ እንደ ምንም እየተጠነ
ቀቀች ቀስ ብላ ቀና አለች ። እንደ ፈራችው አልሆነም እዳራሹ ውስጥ ያሉት ተማሪዎች በሁኔታው እየሳቁ ምግባቸውን ከማጣጣም በስተቀር እነትዕግሥትን ልብ ብለው አልተመለከቷቸውም ።
የበሉ!ትን ትሪ ሳያነሱ ፥ ግራ ቀኝ ሳይመለከቱ ሁለቱም አንገታቸውን እቅርቅረው ፈትለክ ብለው ወጡ ።
ከቀትር በኋላ ወደ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ ፥ እስክንድር ከመኝታ ክፍሉ ተጠራ ። አልጋው ላይ ጋደም ብሎ እያነበቀ
ነበር።
ማን ነው የፈለገኝ ? አለው : ተልኮ የመጣውን አንዲት ልጅ ናት ። ወደዚህ ስመጣ አይታኝ አንተን እንድጠራላት ጠየቀችኝ ።
“ ስሜን የምታውቅ ናት ? ”
“ እሷ፡ ስምህን ጠርታ ነው ንገርልኝ ያለችኝ
በፈጣን ርምጃ ከመኝታ ክፍሉ ወጥቶ ፥ ደረጃውን ወርዶ ወደ ውጪ ብቅ ሲል ማርታ ደመቀን ቆማ ተመለከታት »
ግር አለው ። ከአሁን በፊት ግቢው ውስጥ መታየት ካልሆነ በስተቀር ንግግር አልነበራቸውም።
ማርታ እሷ እንዳስጠራችው እንዲያውቅ ፈገግ አለችለት ። ዝብርቅርቅ ባለ ስሜት ልቡ እየነጠረ ቀረባት ።
እኔ ጋ ነው ? ” አላት የውስጥ ስሜቱን በሚገልጽ ጣፋጭ ቅላጼ ።
“አዎ! ስለ አቤል ልጠይቅህ ነው ” አለችው ዕዝን ብላ።
የአቤልንም የእኔንም ስም እንዴት አወቀች ? ” ሲል አሰበ ። ወዲያው ግን ለምን ጅል እሆናለሁ ? እኔ እራሴ
የእሷንና የትዕግሥትን ስም አጣርቼ ዐውቅ የለም እንዴ ! የእነሱ ማወቅ ያስደንቃል ? እንዲያውም ለወሬ ሴቶች ይብሳሉ ” አለ ፡ ባይነጋገሩም በዐይን እየተራረፉ የተላለፉበትን ቀን በልቡ እያስታወሰ ።
እንደ ሴትነቷ ስማቸውን ዐውቃ እንዳላወቀች ለመሆን አለመሞከሯ አስደነቀው ። አመጣጧ ብዙ ነገር ጭንቅላቱ ውስጥ አተረማመሰበት ። የተጠቀለለ ነገር ይዛለች ።
ትዕግሥት ራሷ መምጣት ፈርታ ልካት ይሆን?” ሲል አሰበ ። በምግብ አዳራሽ ውስጥ ለአቤል መውደቅ መንስኤው
ከእነሱ ጋር እንደ ተያያዜ ፈጽሞ አላወቀም ነበር ።
ምግብ ቤት ውስጥ ሲወድቅ ነበርሽ እንዴ ? ” አላትና ፥ ከእሷ መልስ ሳይጠብቅ ። የትኩሱ ወጥ ፍንጣቂ
እጁን ትንሽ ጠበሰው እንጂ ሌላ ቦታ አልተጎዳም ” አላት ።
ከንፈሯን መጠጠች
“ እምልሽ ፡ መቼም እዚያ ሁሉ ተማሪ መሐል መውደቁ ራሱ ሕመም ነው ። አለ አይደል ! የአጋጣሚ ነገር ቢሆንም ያሳፍራል ። እና በድንጋጤ ትንሽ ተረብሾ ፡ ምሳውንም ባመጣለት ሊበላ ኣልቻለም ። አሁን ተኝቷል ። ድንጋጤው ሲያልፍለትና ሁኔታው ሲረሳው ደኅና ይሆናል አላት »
እንደ ገና ከንፈሯን መጠጠችና “ ውይ በናትህ 'አወዳደቁ እንዴት ሰቀጠቅጠኝ መሰለህ ! ብቻ እንኳን ተረፈ አለችው ።
አስተዛዘኗ ልቡን ነካው ። ምነው እኔ በወደቅኩና እንዲህ ባዘንሽልኝ ! ” አለ በሐሳቡ ።
💥ይቀጥላል💥
👍3❤1
#የታካሚው_ማስታወሻ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
“አዎ፣ ወደዛ ቤት እየሄድኩ እንደሆነ ሳስብ...” ከቤተሰብ ጋር መሆን ታክቷታል፡፡
“አይዞሽ ሃኒዬ፡፡ በቃ እርሻቸው፡፡ እንደሌሉ አስቢያቸው::እንዳልሰማሽ እለፊያቸው፡፡”
“አይ ያቡ፣ እንደዛ ሳልሞክር ቀርቼ መሰለህ? የሚቻል አይደለም፡፡ ከባድ ነው፡፡ በተለይ ታላቅ እህት ተብዬዋ፣ እዛ ሆኜ ስንት ነገር እንዳላደረኩላት ዛሬ የምትናገረኝ ቅስሜን እስኪጠዘጥዘኝ ድረስ ነው፡፡ ነገሩ ልብን ይሰብራል፡፡” ስታወራ እንባዋ መጣ፡፡ ወሬውን
አስቀይሬ መቀባጠር ጀመርኩ፡፡ ሞጆን አልፈን ወደ ቢሾፍቱ ስንጠጋ፤
“ያቡዬ..?” አለችኝ ምቀባጥረውን አቋርጣኝ፡፡
“ወዬ ሃን...”
“አንተ ግን ለምን አታገባም?”
“ማለት...?” ተደናበርኩ፡፡ ያላሰብኩት ዱብዳ ነው፡፡
“ብቻህን ነው ምትኖረው፡፡ በዛ ላይ የቅርብ ሰው እንኳ ባጠገብህ የለም፡፡ ስለዚህ ለምን አንዷን አታገባም?”
“እ...፣ እሱስ እውነትሽን ነው፡፡ ግን..”
“ይኼ ምን ግን ያስፈልገዋል?” ሳይታወቃት ጮኸች፡፡
“ንሮዬን እያየሽው አይደል፡፡ ገና ለመቆም ድክ ድክ እያልኩ፡፡ባይሆን ስራው መስመር ከያዘልኝ በኋላ...”
ቁርጠኝነቱ ቢኖርህ፣ አሁን እዚህ በሳምንት ያወጣነው፣ለሁለት ሰው ንሮን ለመመስረት በቂ ነው፡፡ አቅም ሳይሆን ቁርጠኝነቱ ነው የሌለህ፡፡”
የምመልሰው አልነበረኝም፡፡ ዝም አልኩ፡፡ እርሷም ዝም አለች፡፡መናኸሪያ እስክንደርስ ምንም አላወራንም፡፡
ወደየቤታችን ከመለያየታችን በፊት አቀፍኳትና፣
“አይዞሽ የኔ ፍቅር፣ ሁሉ ነገር ይገባኛል፡፡ እረዳሻለሁኮ፡፡ ጠንከር በይ፡፡ ትንሽ ግዜ ብቻ ታገሺኝ፣” ጉንጫን ሳምኳት፡፡ ከልቤ ነበር ያልኳት። ከሷ በፊት ስለማንም ደንታ ተሰምቶኝ አያውቅም፡፡ ማታ እንዴት እንደሆነች ደውዬ ጠየኳት፡፡እንደተለመደው ነው አለችኝ፡፡
ከአርባምንጭ መልስ የኔ ስሜት ጥሩ ሆኗል፡፡ የሃኒ ደግሞ ጭራሽ ብሶባታል፡፡ በስልክም በአካልም መነፍረቅ አመሏ ሆኗል፡፡ ድብርቱ እንዳይጋባብኝ፣ በየቀኑ ውሎዬን ከነ ሃብትሽ ጋር አደረኩ፡፡
ዛሬም፣ ለአራተኛ ቀን ምሳ እየበላን፣ ጃምቦ እየላፍን፣ ከአርባምንጭ
የተረፈ ወሬ አየገረብን ነው፡፡ መሃል ላይ ወሬው ሲቀዘቅዝ፣ ሳሚ ትዝ አለኝ፡፡ ተጠፋፍተናል፡፡ ደወልኩለት፣
ሳሚሻ የጠፋ ሰው፣ እንዴት ነው ባክህ?” አልኩት፡፡
ጎረምሳው፣ በዚህ ፍጥነት ሰው ትረሳለህ?”
“እውነት ሳሚሻ ቢዚ ሆኜ ነው፡፡ ብረሳ፣ ብረሳ አንተን እረሳለሁ?” ተጎዘጎዝኩኝ፡፡
“እኔ ምልህ፣ የአለቃህን ነገር ሰማህ?”
“የትኛው አለቃዬ? ሼባው?”
“አዎ ሼባው፡፡”
“ኧረ ምንም አልሰማሁም፡፡ ምን ተፈጠረ?”
“ጮማ ወሬ አምልጦሃላ..?” ካ..ካ..ካ... የተለመደች ካንገት በላይ ሳቁን፡፡
“ይነገረኛ! እዛ የቀረኸኝ ዘመድ አንተ ብቻ ነህ፡፡ ማን ይነግረኛል ብለህ ነው?”
“ያቺ ጉደኛ ሜሪ፣ ሼባውን ጉድ ሰራችው፡፡ እሷን ሊያገባ ሚስቱን ፈታ::”
“ምን?” ጆሮዬን አላመንኩም፡፡
“አዎ፡፡ ፍርድ ቤት ፍቺ ጨርሰው፣ ንብረት በሽማግሌ ተካፈሉ ሲባሉ፣ ሽማግሌ ሁነኝ አይለኝም?”
“በጣም ሚገርም ነገር ነው የምትነግረኝ፡፡ ግን ቆይ፣ ሚሪ እሺ
ባትለውስ? አባቷን የሚያህል ሽማግሌ፣ ምን አጥታ ነው ምታገባው? እሺ ደግሞ ልጆቹስ?” ሁሉ ነገር ግራ ገባኝ፡፡
“ልጆቹን ምን ሊደርግ እንዳሰበ እኔ አላውቅም፡፡ ሜሪ ግን ከቤተሰቧጋ ወጥታ ተከራይቶላት ካስቀመጣት ቆየ፡፡ እሱንም
አልሰማህማ? ከብዙ መረጃዎች እርቀሃላ ወንድሜ፡፡” ካካካ...፡፡ ብዙ ከተጫወትን በኋላ፣
“በል እንደዚህ ብዙ መረጃ እንዳያመልጥህ፣ ቶሎ ቶሎ ደውል፡፡
ሲደወልልህም ደግሞ ስልክ አንሳ፤” አለኝ፡፡
“ኧረ እኔው እደውላለሁ፡፡ አዲሱን ስራ መስመር ለማስያዝ በት በት ስል እየረሳውኮ ነው፡፡ አሁን መስመር እየያዘልኝ ነው፡፡ አልጠፋም፧
እደውላለሁ፡፡”
ስልኩን ዘግቼ ለነ ሃብትሽ፣ ስለ ቀድሞ አለቃዬ ሙሉ ታሪኩን ነግሪያቸው፣ በእርሱም በሜሪም ድርጊት ስንገረም አመሸን፡፡ ማታ እቤቴ ስገባ እንደተለመደው ለሃኒ ልደውል ስልኬን ሳወጣ፣ በጣም ብዙ ግዜ ደውላ ነበር፡፡ ወሬ ይዘን አልሰማነውም፡፡ የቴክስት መልዕክት ልካልኛለች፡፡ ስለሁሉም ነገር አመሰግናለሁ!” ይላል፡፡ መልሼ ደጋግሜ
ደወልኩላት፡፡ ስልኳ ዝግ ነው፡፡ እንቅልፌን ተኛሁ፡፡ ጠዋት ስነሳ እጅግ አስደንጋጭ ዜና ሰማሁ፡፡ ሃኒ ትናንት ማታ መርዝ ጠጥታ እራሷን አጠፋች፡፡ ማመን አልቻልኩም፡፡ አዞረኝ፡፡ በቀጥታ እቤታቸው ሄድኩኝ፡፡ ሃኒ እራሷን ማጥፋቷ እውነት ነው፡፡ ቤታቸው በለቀስተኛ
ተሞልቷል፡፡ አብዛኛው የሰፈር ሰው በጣም አዝኗል፣ ከልቡ ያለቅሳል፡፡
ማያለቅስ ለቀስተኛ ማግኘት ከባድ ነው፡፡ ለነገሩ ባያዝኑና ባያለቅሱ ነበር ሚገርመው፡፡ ገና በልጅነቷ ነው የተቀጨችው ፤ በዛ ላይ ምታጓጓ ቆንጅ።
ነበረች፡፡ መሞቷ፣ እራሷን ማጥፋቷ ያላስደነገጠው የለም፡፡ አልቅሺ አልወጣልህ አለኝ፡፡ ሃዘኑ ቅስሜን ሰርስሮ ገባ፡፡ ከቀብሯ ጀምሮ እስከሰልስት፣ የሚያቀኝ ሰው ባይኖርም፣ ከለቀስተኛው መሃል ሆኜ ስቅስቅ ብዬ አነባሁ፡፡ ልቤ በሃዘን ተሰበረ፡፡ ከፍተኛ ጫና እንዳለባት
አውቅ ነበር፡፡ በተለይ ታላቅ እህቷን እንደገዳይ አየኋት፡፡ ስታለቅስ አይቻት፣ ለቅሶና ሃዘኗን አስመሳይ የአዛ እንባ ሆነብኝ፡፡ ሄጄ ማነቅ አሰኘኝ፡፡ ያስጨንቋት እንደነበር ተረድቼ ነበር፡፡ እራሷን እስክታጠፋ ይደርሳል ብዬ ግን በፍፁም አልገመትኩም፡፡ ልደርስላት፣ ልከላከላት
ይገባ ነበር፡፡ ከኔ ውጪ የሚረዳት፣ ሚከላከልላት፣ ሚደርስላት ሰው
አልነበራትም፡፡ እንዳግዛት ነግራኝ ነበር፡፡ አብረን እንኑር ብላኝ ነበር፡፡አልተረዳኋትም፤ አልደረስኩላትም፡፡ ላድናት ስችል አላደረኩትም፡፡
ልረሳው የማልችለው ከባድ ሃዘን በውስጤ ነገሰብኝ፡፡
ከሞተች ሦስት ሳምንት ሙሉ በዚህ ስሜት ተሰቃየሁ። በአዕምሮዬ መልስ የሌላቸው ጥያቄዎች ይዘንባሉ፡፡ ለምንድን ነው ህይወት እንዲህ ግራ የሆነችብኝ? ለምንድነው ተስፋዬ በተደጋጋሚ እየበራ ሚጠፋው? ለምንድን ነው በተደጋጋሚ ሚጨልምብኝ? ሃኒ
ደስተኛ አድርጋኝ ነበረ፡፡ የምኖርላት ምክንያቴ ሆና ነበረ፡፡ ለምን እርሷን
ይወስድብኛል? ለምን? ለምን? ለምን?! የማያባሩ ጥያቄዎች፣ ልሸከመው፣ ልቋቋመው የማልችለው የልብ ስብራት፡፡
እራሴን በአልኮል ደብቁ ለማለፍ ሞከርኩ፡፡ ጭንቀትና ድባቴው ግን እየባሰብኝ መጣ፡፡ህይወት መልሳ እንደቀድሞው ባዶና ተስፋ ቢስ ሆነችብኝ፡፡ ልቋቋመው ማልችለው ፀፀት ያላምጠኛል፡፡ ስልኩን ባነሳው ኖሮ ታተርፋት ነበር ይለኛል። በእርሷ ምክንያት፣ የተውኩት፣ የጣልኩት እራሴን የማጥፋት እቅድ፣ አቧራውን አራግፎ፣ የችግሬ የመጀመሪያ ተመራጩ መፍትሄ
ሆኖ ታየኝ፡፡ ተከተላት ይለኛል፡፡ እዕምሮዬ ሌላ ነገር ማሰብ አቁሟል፡፡ በየቀኑ፣ በየሰዐቱ፣ በየደቂቃው ይነተርከኛል፣ ይጠዘጥዘኛል፡፡ ከዚች ጭለማ ህይወት ሞት በስንት ጠዓሙ ይለኛል፡፡ በስተመጨረሻ ተሸነፍኩለት፡፡ የተውኩትን እቅዴን በድጋሜ በጥንቃቄ ለመፈፀም
መዘጋጀት ጀመርኩኝ፡፡ በእጄ ከቀረኝ ገንዘብ አብዛኛውን ለእናቴ ላኩላት፣ የዶሮ ቤቱን ለነ ሃብትሽ እንደባለፈው ሰው እንዲያመጡና እንዲከታተሉት አደረኩኝ፡፡
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
“አዎ፣ ወደዛ ቤት እየሄድኩ እንደሆነ ሳስብ...” ከቤተሰብ ጋር መሆን ታክቷታል፡፡
“አይዞሽ ሃኒዬ፡፡ በቃ እርሻቸው፡፡ እንደሌሉ አስቢያቸው::እንዳልሰማሽ እለፊያቸው፡፡”
“አይ ያቡ፣ እንደዛ ሳልሞክር ቀርቼ መሰለህ? የሚቻል አይደለም፡፡ ከባድ ነው፡፡ በተለይ ታላቅ እህት ተብዬዋ፣ እዛ ሆኜ ስንት ነገር እንዳላደረኩላት ዛሬ የምትናገረኝ ቅስሜን እስኪጠዘጥዘኝ ድረስ ነው፡፡ ነገሩ ልብን ይሰብራል፡፡” ስታወራ እንባዋ መጣ፡፡ ወሬውን
አስቀይሬ መቀባጠር ጀመርኩ፡፡ ሞጆን አልፈን ወደ ቢሾፍቱ ስንጠጋ፤
“ያቡዬ..?” አለችኝ ምቀባጥረውን አቋርጣኝ፡፡
“ወዬ ሃን...”
“አንተ ግን ለምን አታገባም?”
“ማለት...?” ተደናበርኩ፡፡ ያላሰብኩት ዱብዳ ነው፡፡
“ብቻህን ነው ምትኖረው፡፡ በዛ ላይ የቅርብ ሰው እንኳ ባጠገብህ የለም፡፡ ስለዚህ ለምን አንዷን አታገባም?”
“እ...፣ እሱስ እውነትሽን ነው፡፡ ግን..”
“ይኼ ምን ግን ያስፈልገዋል?” ሳይታወቃት ጮኸች፡፡
“ንሮዬን እያየሽው አይደል፡፡ ገና ለመቆም ድክ ድክ እያልኩ፡፡ባይሆን ስራው መስመር ከያዘልኝ በኋላ...”
ቁርጠኝነቱ ቢኖርህ፣ አሁን እዚህ በሳምንት ያወጣነው፣ለሁለት ሰው ንሮን ለመመስረት በቂ ነው፡፡ አቅም ሳይሆን ቁርጠኝነቱ ነው የሌለህ፡፡”
የምመልሰው አልነበረኝም፡፡ ዝም አልኩ፡፡ እርሷም ዝም አለች፡፡መናኸሪያ እስክንደርስ ምንም አላወራንም፡፡
ወደየቤታችን ከመለያየታችን በፊት አቀፍኳትና፣
“አይዞሽ የኔ ፍቅር፣ ሁሉ ነገር ይገባኛል፡፡ እረዳሻለሁኮ፡፡ ጠንከር በይ፡፡ ትንሽ ግዜ ብቻ ታገሺኝ፣” ጉንጫን ሳምኳት፡፡ ከልቤ ነበር ያልኳት። ከሷ በፊት ስለማንም ደንታ ተሰምቶኝ አያውቅም፡፡ ማታ እንዴት እንደሆነች ደውዬ ጠየኳት፡፡እንደተለመደው ነው አለችኝ፡፡
ከአርባምንጭ መልስ የኔ ስሜት ጥሩ ሆኗል፡፡ የሃኒ ደግሞ ጭራሽ ብሶባታል፡፡ በስልክም በአካልም መነፍረቅ አመሏ ሆኗል፡፡ ድብርቱ እንዳይጋባብኝ፣ በየቀኑ ውሎዬን ከነ ሃብትሽ ጋር አደረኩ፡፡
ዛሬም፣ ለአራተኛ ቀን ምሳ እየበላን፣ ጃምቦ እየላፍን፣ ከአርባምንጭ
የተረፈ ወሬ አየገረብን ነው፡፡ መሃል ላይ ወሬው ሲቀዘቅዝ፣ ሳሚ ትዝ አለኝ፡፡ ተጠፋፍተናል፡፡ ደወልኩለት፣
ሳሚሻ የጠፋ ሰው፣ እንዴት ነው ባክህ?” አልኩት፡፡
ጎረምሳው፣ በዚህ ፍጥነት ሰው ትረሳለህ?”
“እውነት ሳሚሻ ቢዚ ሆኜ ነው፡፡ ብረሳ፣ ብረሳ አንተን እረሳለሁ?” ተጎዘጎዝኩኝ፡፡
“እኔ ምልህ፣ የአለቃህን ነገር ሰማህ?”
“የትኛው አለቃዬ? ሼባው?”
“አዎ ሼባው፡፡”
“ኧረ ምንም አልሰማሁም፡፡ ምን ተፈጠረ?”
“ጮማ ወሬ አምልጦሃላ..?” ካ..ካ..ካ... የተለመደች ካንገት በላይ ሳቁን፡፡
“ይነገረኛ! እዛ የቀረኸኝ ዘመድ አንተ ብቻ ነህ፡፡ ማን ይነግረኛል ብለህ ነው?”
“ያቺ ጉደኛ ሜሪ፣ ሼባውን ጉድ ሰራችው፡፡ እሷን ሊያገባ ሚስቱን ፈታ::”
“ምን?” ጆሮዬን አላመንኩም፡፡
“አዎ፡፡ ፍርድ ቤት ፍቺ ጨርሰው፣ ንብረት በሽማግሌ ተካፈሉ ሲባሉ፣ ሽማግሌ ሁነኝ አይለኝም?”
“በጣም ሚገርም ነገር ነው የምትነግረኝ፡፡ ግን ቆይ፣ ሚሪ እሺ
ባትለውስ? አባቷን የሚያህል ሽማግሌ፣ ምን አጥታ ነው ምታገባው? እሺ ደግሞ ልጆቹስ?” ሁሉ ነገር ግራ ገባኝ፡፡
“ልጆቹን ምን ሊደርግ እንዳሰበ እኔ አላውቅም፡፡ ሜሪ ግን ከቤተሰቧጋ ወጥታ ተከራይቶላት ካስቀመጣት ቆየ፡፡ እሱንም
አልሰማህማ? ከብዙ መረጃዎች እርቀሃላ ወንድሜ፡፡” ካካካ...፡፡ ብዙ ከተጫወትን በኋላ፣
“በል እንደዚህ ብዙ መረጃ እንዳያመልጥህ፣ ቶሎ ቶሎ ደውል፡፡
ሲደወልልህም ደግሞ ስልክ አንሳ፤” አለኝ፡፡
“ኧረ እኔው እደውላለሁ፡፡ አዲሱን ስራ መስመር ለማስያዝ በት በት ስል እየረሳውኮ ነው፡፡ አሁን መስመር እየያዘልኝ ነው፡፡ አልጠፋም፧
እደውላለሁ፡፡”
ስልኩን ዘግቼ ለነ ሃብትሽ፣ ስለ ቀድሞ አለቃዬ ሙሉ ታሪኩን ነግሪያቸው፣ በእርሱም በሜሪም ድርጊት ስንገረም አመሸን፡፡ ማታ እቤቴ ስገባ እንደተለመደው ለሃኒ ልደውል ስልኬን ሳወጣ፣ በጣም ብዙ ግዜ ደውላ ነበር፡፡ ወሬ ይዘን አልሰማነውም፡፡ የቴክስት መልዕክት ልካልኛለች፡፡ ስለሁሉም ነገር አመሰግናለሁ!” ይላል፡፡ መልሼ ደጋግሜ
ደወልኩላት፡፡ ስልኳ ዝግ ነው፡፡ እንቅልፌን ተኛሁ፡፡ ጠዋት ስነሳ እጅግ አስደንጋጭ ዜና ሰማሁ፡፡ ሃኒ ትናንት ማታ መርዝ ጠጥታ እራሷን አጠፋች፡፡ ማመን አልቻልኩም፡፡ አዞረኝ፡፡ በቀጥታ እቤታቸው ሄድኩኝ፡፡ ሃኒ እራሷን ማጥፋቷ እውነት ነው፡፡ ቤታቸው በለቀስተኛ
ተሞልቷል፡፡ አብዛኛው የሰፈር ሰው በጣም አዝኗል፣ ከልቡ ያለቅሳል፡፡
ማያለቅስ ለቀስተኛ ማግኘት ከባድ ነው፡፡ ለነገሩ ባያዝኑና ባያለቅሱ ነበር ሚገርመው፡፡ ገና በልጅነቷ ነው የተቀጨችው ፤ በዛ ላይ ምታጓጓ ቆንጅ።
ነበረች፡፡ መሞቷ፣ እራሷን ማጥፋቷ ያላስደነገጠው የለም፡፡ አልቅሺ አልወጣልህ አለኝ፡፡ ሃዘኑ ቅስሜን ሰርስሮ ገባ፡፡ ከቀብሯ ጀምሮ እስከሰልስት፣ የሚያቀኝ ሰው ባይኖርም፣ ከለቀስተኛው መሃል ሆኜ ስቅስቅ ብዬ አነባሁ፡፡ ልቤ በሃዘን ተሰበረ፡፡ ከፍተኛ ጫና እንዳለባት
አውቅ ነበር፡፡ በተለይ ታላቅ እህቷን እንደገዳይ አየኋት፡፡ ስታለቅስ አይቻት፣ ለቅሶና ሃዘኗን አስመሳይ የአዛ እንባ ሆነብኝ፡፡ ሄጄ ማነቅ አሰኘኝ፡፡ ያስጨንቋት እንደነበር ተረድቼ ነበር፡፡ እራሷን እስክታጠፋ ይደርሳል ብዬ ግን በፍፁም አልገመትኩም፡፡ ልደርስላት፣ ልከላከላት
ይገባ ነበር፡፡ ከኔ ውጪ የሚረዳት፣ ሚከላከልላት፣ ሚደርስላት ሰው
አልነበራትም፡፡ እንዳግዛት ነግራኝ ነበር፡፡ አብረን እንኑር ብላኝ ነበር፡፡አልተረዳኋትም፤ አልደረስኩላትም፡፡ ላድናት ስችል አላደረኩትም፡፡
ልረሳው የማልችለው ከባድ ሃዘን በውስጤ ነገሰብኝ፡፡
ከሞተች ሦስት ሳምንት ሙሉ በዚህ ስሜት ተሰቃየሁ። በአዕምሮዬ መልስ የሌላቸው ጥያቄዎች ይዘንባሉ፡፡ ለምንድን ነው ህይወት እንዲህ ግራ የሆነችብኝ? ለምንድነው ተስፋዬ በተደጋጋሚ እየበራ ሚጠፋው? ለምንድን ነው በተደጋጋሚ ሚጨልምብኝ? ሃኒ
ደስተኛ አድርጋኝ ነበረ፡፡ የምኖርላት ምክንያቴ ሆና ነበረ፡፡ ለምን እርሷን
ይወስድብኛል? ለምን? ለምን? ለምን?! የማያባሩ ጥያቄዎች፣ ልሸከመው፣ ልቋቋመው የማልችለው የልብ ስብራት፡፡
እራሴን በአልኮል ደብቁ ለማለፍ ሞከርኩ፡፡ ጭንቀትና ድባቴው ግን እየባሰብኝ መጣ፡፡ህይወት መልሳ እንደቀድሞው ባዶና ተስፋ ቢስ ሆነችብኝ፡፡ ልቋቋመው ማልችለው ፀፀት ያላምጠኛል፡፡ ስልኩን ባነሳው ኖሮ ታተርፋት ነበር ይለኛል። በእርሷ ምክንያት፣ የተውኩት፣ የጣልኩት እራሴን የማጥፋት እቅድ፣ አቧራውን አራግፎ፣ የችግሬ የመጀመሪያ ተመራጩ መፍትሄ
ሆኖ ታየኝ፡፡ ተከተላት ይለኛል፡፡ እዕምሮዬ ሌላ ነገር ማሰብ አቁሟል፡፡ በየቀኑ፣ በየሰዐቱ፣ በየደቂቃው ይነተርከኛል፣ ይጠዘጥዘኛል፡፡ ከዚች ጭለማ ህይወት ሞት በስንት ጠዓሙ ይለኛል፡፡ በስተመጨረሻ ተሸነፍኩለት፡፡ የተውኩትን እቅዴን በድጋሜ በጥንቃቄ ለመፈፀም
መዘጋጀት ጀመርኩኝ፡፡ በእጄ ከቀረኝ ገንዘብ አብዛኛውን ለእናቴ ላኩላት፣ የዶሮ ቤቱን ለነ ሃብትሽ እንደባለፈው ሰው እንዲያመጡና እንዲከታተሉት አደረኩኝ፡፡
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍3
#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
አስተዛዘኗ ልቡን ነካው ። ምነው እኔ በወደቅኩና እንዲህ ባዘንሽልኝ ! ” አለ በሐሳቡ ።
ልቡ ስለተረጋጋ ዐይኖቹ ውበቷን ከላይ እስከ ታች ማስተዋል ይዘው ነበር ። አፍንጫውም ከትኩሳቷ ጋር የሚተነውን ሽቶ መቀበል ጀምሯል ። ስትናገር ትንፋሿ ራሱ ሽቶ የመሰለውን ። ከእሑድ የሠርግ አለባበሷና አካኳሷ ከፊሉ ላይዋ ላይ ቀርቶ ነበር ። በአንገተ ክፍቱ ሹራቧ በኩል የተላጠ ሽንኩርት መስለው ብቅ ያሉት ጡቶቿ ከእስክንድር ዐይን ጋር ተፋጠጡ ።ጡት መያዛ አላደረገችም ነበር ።
“ ይህንን ለአቤል ነው ያመጣሁለት ” አለችና " ይዛው የነበረውን የተጠቀለለ ነገር ሰጠችው ። ኬክ ገዝታ ለት ነበር ።
እስክንድር የባሰውን ድንግርግር አለ ። ይህን ለሚያህል ውለታ የሚያበቃ ግንኙነት ነበር ማለት ነው ? ” አለ
በልቡ ።አቤልን ጠረጠረው ። ሆኖም ከማርታ ጋር አቀራርቦ ያነጋገረውን ይህን አጋጣሚ ወደደው ።
ኬኩን ሰጥታው ጥቂት መንገድ ከሔደች በኋላ ፥ በአንዳች ግፊት ተስባ ዘወር ስትል እንዳጋጣሚ እስክንድርም የዞረባት ቅጽበት ስለ ነበረች ዐይን ለዐይን ተገጣጠሙ ።ሁለቱም ተፋፍረው ፊታቸውን ወደ መንገዳቸው መለሱ ።
እስክንድር ኬኩን ይዞ ወደ መኝታ ክፍሉ ሲመለስ “ጆኒ ለካ የዋህ ስትመስል ፥ ውስጥ ውስጡን ጉዳይዋን አጠና
ክራለች ” እያለ አቤልን በልቡ እያማው ነበር ።
ከክፍሉ እንደ ገባ አቤልን አስነሣውና ፥ “ ቀና በል እባክህን ፤ ጣፋጭ ምግብና ጣፋጭ ወሬ አምጥቼሃለሁ ”አለውና ፥ በችኮላ እሽጉን ፈትቶ አንድ ኬክ አውጥቶ
ለራሱ ገመጠ ።
አቤል ለምንም ነገር ባልጓጓ ስሜት ተወኝ እባክህ እስክንድር ፥ ምንም አልፈልግም ብተኛ ይሻለኛል ” አለው ። ፊቱን ትራሱ ላይ እንደ ደፋ ነበር
እስክንድር ሌላ ኬክ አውጥቶ ፡ ጓደኝነት በተሞላው ስሜት ፡ “ ኤጭ !አንቺ ደሞ እንዲያው በቀላል ነገር መብሸቅ ይቀናሻል ። ተደናቅፎ መውደቅ በማንም ላይ ሊደርስ የሚችል አጋጣሚ ነው ። ይልቅ ተነሽና ይህችን ነገር
ግመጭ፥” አለው
አቤል ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ዝም !
እስክንድር ነገሩን ለማቅለል ያህል ብቻ ሳይሆን በጊዜው ያስደንግጥ እንጂ በእርግጥም ቀላል ነው ብሎ ነው
የገመተው የአቤል ምላሽ ግን ጠነከረበት
ትንሽ ቆየና ፡ ዘዴ ያገኘ ወይም አቤልን ከመጥፎ ስሜቱ ያዘናጋ መስሎት ፡ እረ ሌላው ቢቀር ውቃቢዋ ያይሃል !
ይበላልኛል ብላ ደክማ አምጥታልህ ” አለና ሳይጨርስ እቤል አቋረጠው ።
“ እንዴ ኬኩን ማነው ያመጣውን ? ” አለ አበል ጉጉት ባዘለ ደካማ ድምፅ ፥ ቀስ ብሎ ፊቱን ከደፋበት ትራስ አነሣ ። ምሳውን አልበላ ስላለው ኬኩን እስክንድር ራሱ ገዝቶ ያመጣለት መስሎት ነበር ።
“ ማርታ ' ኮ ነች ያመጣችልህ ” አለ እስክንድር ስሟን ሲጠራ አንዳች ነገር ሽምቅቅ እያረገው ።
“ እ? ! ” የድንጋጤም ፡ የመገረምም ነበር
ማርታ የ...የእንትና ጓደኛ የትዕግሥትን ስም በአቤል ፊት መጥራት አልፈለገም ።
አቤል ግን ወዲያው ገባው ። ሥሮቹ ተገታትረው ዐይኑ ደም መሰለ
“ በናትህ ስሟን አትጥራብኝ ” አለው ፡ ምርር ባል አነጋገር ፡ “ እሷን ልጅ ላለማየት ስል ይህን ዩኒቨርስቲ ሳልለቅ አልቀርም ። ”
እስክንድር ነገሩ ተምታታበት ። ትዕግሥትን ወይስ ማርታን ? ማንኛቸውን ላለማየት ? ” አለ በልቡ የቀድሞም
ጥርጣሬው የተሳሳተ መሰለው ። የሚናገረው ነገር ጠፍቶት
ዝም አለ።
ክፉኛ የቀሉት የአቤል ዐይኖች የታመቀ እንባ ተዘርግፎ እዳይፈስ ትንቅንቅ መያዛቸውን እስክንድር ገመተ ግቢ ነፍስ ውጪ ነፍስ ክፉኛ አሳዘነው ። የሆነ ነገር ልደብቅ ብላ ከውስጥ የምትቃጠለው የምትብከነከነውና የምትጨሰው ሕይወቱ ውስጥ ውስጡን አምርራ ስታለቅስ
በስሜቱ ታየው ። ትካዜው ተጋባበት ። እናም ዝም ብሎ መቆየት አልቻለም ።
ስማ እቤል ልረዳህ የምችለው ነገር ካለ ስሜትህን ሳትደብቅ በንጹሕ የጓደኝነት መንፈስ ንገረኝ ። ሰትጨነቅ ማየት አልፈልግም ። የፈለገው ነገር ይሁን ፡ እሰዋልሃለው
እስክንድር ከአቤል ጋር ከተዋወቀበት ጊዜ ጀምሮ እንዲህ አምርሮና በትካዜ ተመስጦ ሲናገር፥ የመጀመሪያ ጊዜው
ነበር ። ከማርታ ጋር መተዋወቄ ከትዕግሥት ጋር አስተዋውቆኝ ፥ የአቤልን ችግር እፈታለት ይሆናል የሚል እምነት
ስላደረበት እሠዋልሃለሁ” ያለው ከዚህ ተነሥቶ ነበር።
የእስክንድር ወንድማዊ የንግግር ቃና የአቤልን ልብ ክፉኛ ኮረኮረው ። በተለይ “እሠዋልሃለሁ” የምትለዋ ቃል
ከእስክንድር አፍ የወጣችው እንባ በተናነቀው ስሜት ስለ ነበር፡ የልቡን አንጀት በኀዘን ፍላጻ ወጋችው " የሆነ ነገር
ሊነግረው ፈለገ ። ግን ምን ? አፉን ከማጥፋት በስተቀር እስክንድር መፍትሔ የሚያገኝለት አልመሰለውም።
ምንም አልተናገረም መልሶ ፊቱን ከትራሱ ላይ ደፋው።
አንተ ከባድ አርገህ የወሰድከው ነገር ይሄኔ በቀላሉ የሚፈታ ይሆናል ” አለው እስክንድር ።
አቤል አልመለስም ።
“ ስማ እንጂ አቤል ! እባክህ ንገረኝ ፤ ዝም ብለህ ራስህን አታስጨንቅ። ሐሳብን ለሰው ማካፈል ራሱ ከሕመም ያድናል ፡ መጥፎ ተፈጥሮ ነው ያለህ ፡ ለምን ሁሉን ነገር በግልህ ለመወጣት ትሞክራለህ ? ሰው ያስፈልግሃል ! እንግዲያው የጓደኝነት ትርጉሙ ምንድነው ? ነገር ሆድ ውስጥ መጨነቅ መጥፎ ነው ” አለው ፥ በእርግጥም የሚያስከትለው መጥፎ ውጤት እየታየውና መምህር ዮናታን የነግ
ሩት እየታወሰው ።
ስለ እሱ ሕመም እስክንድር ይህን ያህል መጨነቁ ሆዱን ስላባባው አቤል ቀና ብሎ ተወኝ እባክህ እስክንድር ሰለ እርዳታህ አመሰግናለሁ ። የእኔ ሕሙም ግንመፍትሔ የለውም " አትድከም ” ሊለው ፈልጎ ነበር " ነገር ግን እንባው ቀድሞም ዝርግፍ ስላለ መናገር አልቻለም ።ፊቱን ትራሱ ላይ እንደ ደፋ አለቀሰ ። ትዕግሥት ከፊቱ ቆማ በንቀት ፡ “ አልቃሻ ወንድ!” የምትለው መሰለው " ማርታ በእንባው የምትቀልድበት ከት ከት ብላ የምትሥቅበት መሰለው ።
“ ስማ ፡ አቤል ...!” እስክንድር ቢቸግረው ትከሻውን ነቀነቀው ።
መልስ የለም
አቤል ...
ዝም !
እስክንድር በሽቆ ሲጋራውን አውጥቶ ለኮሰና ፥ በልቡ ቤሽቲያ ! የራስህ ጉዳይ ነው ! ” ብሎ ጥሎት ወጣ ።
አንድ የተፈጥሮ ሳይንስ ምሩቅ መምህር ለድኅረምረቃ የሚያበቃውን የጥናት ጽሑፍ መዘክር ከማቅረቡ በፊት አማካሪው ዶክተር አጥናፉ የስንዴ ተክሉን እንዲጎበኙለት ጋበዛቸው ። ፕሮጄክቱን የሚሠራው በስንዴ ተክል ነበር የተለያየ አፈር በስንዴ አበቃቀል ላይ የሚኖረውን ተጽዕኖ አጥንቶ ለማቅረብ ።
ዮናታን ጉዳዩ ባይመለከታቸው ፕሮጄክቱን አቅራቢው መምህር በግል ወዳጅነቱ እንዲ ያዩለት ስለ ጋበዛቸው ከዶክተር አጥናፉ ጋር ሔደው ነበር ። ለጥናት ተክሎች ከተሠራችው ጎጆ ውስጥ እንደገቡ በጣሳ ጉች ጉች ብለው የተቀመጡትን የስንዴ ተክሎች አትኩረው መጐብኘት ጀመሩ ። ከምስታመት ቤቷ ላይ አረንጓዴው ቀለም ሙልጭ ብሎ ስለጠፋ ቃጠሎው ሌላ ከተማ የገቡ ይመስል ነበር ።
“ ለምን የዚህች ጎጆ ስም ተቀይሮ የኋይት ሀውስ ? አይባልም !” አሉ ዮናታን በቀልድ ዐይነት ነገር ግን ወቀሳን ባዘለ አነጋገር ። አረንጓዴው ቀለም ከጠፋ በኋላ
“ ግሪን ሀውስ ” ማለቱ ትርጉመ ቢስ መሆኑን ለመጠቆም ነበር ። “ ኋይት ሀውስ” እንዳይባልማ የተክሏን ጎጆ ከአ
ሜሪካን ቤተ መንግሥት ጎን ማስቀመጥ ይሆናላ ” አሉ ዶክተር አጥናፉ፡ ቀልድን በቀልድ በመመለስ ምንም አስተያየት ሳይሰጡ ስምንት የተክል ቆርቆሮ
ዎች ማለፋቸው አስጎብኝውን ሳያበሽቀው አልቀረም ። ከጎሳ ከኋላቸው
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
አስተዛዘኗ ልቡን ነካው ። ምነው እኔ በወደቅኩና እንዲህ ባዘንሽልኝ ! ” አለ በሐሳቡ ።
ልቡ ስለተረጋጋ ዐይኖቹ ውበቷን ከላይ እስከ ታች ማስተዋል ይዘው ነበር ። አፍንጫውም ከትኩሳቷ ጋር የሚተነውን ሽቶ መቀበል ጀምሯል ። ስትናገር ትንፋሿ ራሱ ሽቶ የመሰለውን ። ከእሑድ የሠርግ አለባበሷና አካኳሷ ከፊሉ ላይዋ ላይ ቀርቶ ነበር ። በአንገተ ክፍቱ ሹራቧ በኩል የተላጠ ሽንኩርት መስለው ብቅ ያሉት ጡቶቿ ከእስክንድር ዐይን ጋር ተፋጠጡ ።ጡት መያዛ አላደረገችም ነበር ።
“ ይህንን ለአቤል ነው ያመጣሁለት ” አለችና " ይዛው የነበረውን የተጠቀለለ ነገር ሰጠችው ። ኬክ ገዝታ ለት ነበር ።
እስክንድር የባሰውን ድንግርግር አለ ። ይህን ለሚያህል ውለታ የሚያበቃ ግንኙነት ነበር ማለት ነው ? ” አለ
በልቡ ።አቤልን ጠረጠረው ። ሆኖም ከማርታ ጋር አቀራርቦ ያነጋገረውን ይህን አጋጣሚ ወደደው ።
ኬኩን ሰጥታው ጥቂት መንገድ ከሔደች በኋላ ፥ በአንዳች ግፊት ተስባ ዘወር ስትል እንዳጋጣሚ እስክንድርም የዞረባት ቅጽበት ስለ ነበረች ዐይን ለዐይን ተገጣጠሙ ።ሁለቱም ተፋፍረው ፊታቸውን ወደ መንገዳቸው መለሱ ።
እስክንድር ኬኩን ይዞ ወደ መኝታ ክፍሉ ሲመለስ “ጆኒ ለካ የዋህ ስትመስል ፥ ውስጥ ውስጡን ጉዳይዋን አጠና
ክራለች ” እያለ አቤልን በልቡ እያማው ነበር ።
ከክፍሉ እንደ ገባ አቤልን አስነሣውና ፥ “ ቀና በል እባክህን ፤ ጣፋጭ ምግብና ጣፋጭ ወሬ አምጥቼሃለሁ ”አለውና ፥ በችኮላ እሽጉን ፈትቶ አንድ ኬክ አውጥቶ
ለራሱ ገመጠ ።
አቤል ለምንም ነገር ባልጓጓ ስሜት ተወኝ እባክህ እስክንድር ፥ ምንም አልፈልግም ብተኛ ይሻለኛል ” አለው ። ፊቱን ትራሱ ላይ እንደ ደፋ ነበር
እስክንድር ሌላ ኬክ አውጥቶ ፡ ጓደኝነት በተሞላው ስሜት ፡ “ ኤጭ !አንቺ ደሞ እንዲያው በቀላል ነገር መብሸቅ ይቀናሻል ። ተደናቅፎ መውደቅ በማንም ላይ ሊደርስ የሚችል አጋጣሚ ነው ። ይልቅ ተነሽና ይህችን ነገር
ግመጭ፥” አለው
አቤል ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ዝም !
እስክንድር ነገሩን ለማቅለል ያህል ብቻ ሳይሆን በጊዜው ያስደንግጥ እንጂ በእርግጥም ቀላል ነው ብሎ ነው
የገመተው የአቤል ምላሽ ግን ጠነከረበት
ትንሽ ቆየና ፡ ዘዴ ያገኘ ወይም አቤልን ከመጥፎ ስሜቱ ያዘናጋ መስሎት ፡ እረ ሌላው ቢቀር ውቃቢዋ ያይሃል !
ይበላልኛል ብላ ደክማ አምጥታልህ ” አለና ሳይጨርስ እቤል አቋረጠው ።
“ እንዴ ኬኩን ማነው ያመጣውን ? ” አለ አበል ጉጉት ባዘለ ደካማ ድምፅ ፥ ቀስ ብሎ ፊቱን ከደፋበት ትራስ አነሣ ። ምሳውን አልበላ ስላለው ኬኩን እስክንድር ራሱ ገዝቶ ያመጣለት መስሎት ነበር ።
“ ማርታ ' ኮ ነች ያመጣችልህ ” አለ እስክንድር ስሟን ሲጠራ አንዳች ነገር ሽምቅቅ እያረገው ።
“ እ? ! ” የድንጋጤም ፡ የመገረምም ነበር
ማርታ የ...የእንትና ጓደኛ የትዕግሥትን ስም በአቤል ፊት መጥራት አልፈለገም ።
አቤል ግን ወዲያው ገባው ። ሥሮቹ ተገታትረው ዐይኑ ደም መሰለ
“ በናትህ ስሟን አትጥራብኝ ” አለው ፡ ምርር ባል አነጋገር ፡ “ እሷን ልጅ ላለማየት ስል ይህን ዩኒቨርስቲ ሳልለቅ አልቀርም ። ”
እስክንድር ነገሩ ተምታታበት ። ትዕግሥትን ወይስ ማርታን ? ማንኛቸውን ላለማየት ? ” አለ በልቡ የቀድሞም
ጥርጣሬው የተሳሳተ መሰለው ። የሚናገረው ነገር ጠፍቶት
ዝም አለ።
ክፉኛ የቀሉት የአቤል ዐይኖች የታመቀ እንባ ተዘርግፎ እዳይፈስ ትንቅንቅ መያዛቸውን እስክንድር ገመተ ግቢ ነፍስ ውጪ ነፍስ ክፉኛ አሳዘነው ። የሆነ ነገር ልደብቅ ብላ ከውስጥ የምትቃጠለው የምትብከነከነውና የምትጨሰው ሕይወቱ ውስጥ ውስጡን አምርራ ስታለቅስ
በስሜቱ ታየው ። ትካዜው ተጋባበት ። እናም ዝም ብሎ መቆየት አልቻለም ።
ስማ እቤል ልረዳህ የምችለው ነገር ካለ ስሜትህን ሳትደብቅ በንጹሕ የጓደኝነት መንፈስ ንገረኝ ። ሰትጨነቅ ማየት አልፈልግም ። የፈለገው ነገር ይሁን ፡ እሰዋልሃለው
እስክንድር ከአቤል ጋር ከተዋወቀበት ጊዜ ጀምሮ እንዲህ አምርሮና በትካዜ ተመስጦ ሲናገር፥ የመጀመሪያ ጊዜው
ነበር ። ከማርታ ጋር መተዋወቄ ከትዕግሥት ጋር አስተዋውቆኝ ፥ የአቤልን ችግር እፈታለት ይሆናል የሚል እምነት
ስላደረበት እሠዋልሃለሁ” ያለው ከዚህ ተነሥቶ ነበር።
የእስክንድር ወንድማዊ የንግግር ቃና የአቤልን ልብ ክፉኛ ኮረኮረው ። በተለይ “እሠዋልሃለሁ” የምትለዋ ቃል
ከእስክንድር አፍ የወጣችው እንባ በተናነቀው ስሜት ስለ ነበር፡ የልቡን አንጀት በኀዘን ፍላጻ ወጋችው " የሆነ ነገር
ሊነግረው ፈለገ ። ግን ምን ? አፉን ከማጥፋት በስተቀር እስክንድር መፍትሔ የሚያገኝለት አልመሰለውም።
ምንም አልተናገረም መልሶ ፊቱን ከትራሱ ላይ ደፋው።
አንተ ከባድ አርገህ የወሰድከው ነገር ይሄኔ በቀላሉ የሚፈታ ይሆናል ” አለው እስክንድር ።
አቤል አልመለስም ።
“ ስማ እንጂ አቤል ! እባክህ ንገረኝ ፤ ዝም ብለህ ራስህን አታስጨንቅ። ሐሳብን ለሰው ማካፈል ራሱ ከሕመም ያድናል ፡ መጥፎ ተፈጥሮ ነው ያለህ ፡ ለምን ሁሉን ነገር በግልህ ለመወጣት ትሞክራለህ ? ሰው ያስፈልግሃል ! እንግዲያው የጓደኝነት ትርጉሙ ምንድነው ? ነገር ሆድ ውስጥ መጨነቅ መጥፎ ነው ” አለው ፥ በእርግጥም የሚያስከትለው መጥፎ ውጤት እየታየውና መምህር ዮናታን የነግ
ሩት እየታወሰው ።
ስለ እሱ ሕመም እስክንድር ይህን ያህል መጨነቁ ሆዱን ስላባባው አቤል ቀና ብሎ ተወኝ እባክህ እስክንድር ሰለ እርዳታህ አመሰግናለሁ ። የእኔ ሕሙም ግንመፍትሔ የለውም " አትድከም ” ሊለው ፈልጎ ነበር " ነገር ግን እንባው ቀድሞም ዝርግፍ ስላለ መናገር አልቻለም ።ፊቱን ትራሱ ላይ እንደ ደፋ አለቀሰ ። ትዕግሥት ከፊቱ ቆማ በንቀት ፡ “ አልቃሻ ወንድ!” የምትለው መሰለው " ማርታ በእንባው የምትቀልድበት ከት ከት ብላ የምትሥቅበት መሰለው ።
“ ስማ ፡ አቤል ...!” እስክንድር ቢቸግረው ትከሻውን ነቀነቀው ።
መልስ የለም
አቤል ...
ዝም !
እስክንድር በሽቆ ሲጋራውን አውጥቶ ለኮሰና ፥ በልቡ ቤሽቲያ ! የራስህ ጉዳይ ነው ! ” ብሎ ጥሎት ወጣ ።
አንድ የተፈጥሮ ሳይንስ ምሩቅ መምህር ለድኅረምረቃ የሚያበቃውን የጥናት ጽሑፍ መዘክር ከማቅረቡ በፊት አማካሪው ዶክተር አጥናፉ የስንዴ ተክሉን እንዲጎበኙለት ጋበዛቸው ። ፕሮጄክቱን የሚሠራው በስንዴ ተክል ነበር የተለያየ አፈር በስንዴ አበቃቀል ላይ የሚኖረውን ተጽዕኖ አጥንቶ ለማቅረብ ።
ዮናታን ጉዳዩ ባይመለከታቸው ፕሮጄክቱን አቅራቢው መምህር በግል ወዳጅነቱ እንዲ ያዩለት ስለ ጋበዛቸው ከዶክተር አጥናፉ ጋር ሔደው ነበር ። ለጥናት ተክሎች ከተሠራችው ጎጆ ውስጥ እንደገቡ በጣሳ ጉች ጉች ብለው የተቀመጡትን የስንዴ ተክሎች አትኩረው መጐብኘት ጀመሩ ። ከምስታመት ቤቷ ላይ አረንጓዴው ቀለም ሙልጭ ብሎ ስለጠፋ ቃጠሎው ሌላ ከተማ የገቡ ይመስል ነበር ።
“ ለምን የዚህች ጎጆ ስም ተቀይሮ የኋይት ሀውስ ? አይባልም !” አሉ ዮናታን በቀልድ ዐይነት ነገር ግን ወቀሳን ባዘለ አነጋገር ። አረንጓዴው ቀለም ከጠፋ በኋላ
“ ግሪን ሀውስ ” ማለቱ ትርጉመ ቢስ መሆኑን ለመጠቆም ነበር ። “ ኋይት ሀውስ” እንዳይባልማ የተክሏን ጎጆ ከአ
ሜሪካን ቤተ መንግሥት ጎን ማስቀመጥ ይሆናላ ” አሉ ዶክተር አጥናፉ፡ ቀልድን በቀልድ በመመለስ ምንም አስተያየት ሳይሰጡ ስምንት የተክል ቆርቆሮ
ዎች ማለፋቸው አስጎብኝውን ሳያበሽቀው አልቀረም ። ከጎሳ ከኋላቸው
👍3
እየተከተለ “ ግሩም ነው ! ” የሚል ድምፅ ይጠብቅ ነበር ።“
ይህ የየት አገር ዐፈር ነው ? ” አሉ ዶክተር አጥናፉ፡ ዐፈሩ በደንብ ተስማምቶአቸው ከሁሉም ፋፍተው የበቀሉትን ዐምስት ያህል የቆርቆሮ ተክሎች እየተመለከቱ
የደብረ ዘይት ዐፊር ነው ” አለ አስጎብኝው ቆርቆሮው ላይ የጻፈውን ኮድ ተመልክቶ ፣ “ ይገርምዎታል ! በአገራችን
የስነንዴ ተክል ርዝመት ውስጥ ከፍተኛውን ደረጃ ሳይዝ አይቀርም ” ብሎ ፥ የዕድገቱን ፍጥነትና ርዝመት
የላከበትን ሰነድ ፍለጋ ማኅደሩን ያገላብጥ ጀመር ።
ፎቶግራፍ አስነሥተኸዋል ? ”
“አላነሳሁትም ። የጅማው ዐፈር ላይ የተተከሉት ፍጥነትም ባይኖራቸው ዕድገታቸውን ስላላቋረጡ ትንሽ
ልጠብቃቸውና ኣንድ ላይ አስነሣቸዋለሁ ብየ ነው ” አለ አስጎውብኝ ፥ ፊተ ብቻ ሳይሆን ልቡም ፈክቶ የፎቶግራፍ
ጥያቄ ለፕሮጄክቱ ፍጻሜ መቃረቢያ ስለሆነ ዶክተር አጥናፉ ይህን ማንሣታቸው በተዘዋዋሪም ሆን በውበቱ እንደረኩ ለመገመት አስችሎታል ።
“ አሁኑኑ ብታስነሣው የሚሻል ይመስለኛል ። ካለበለዚያ የጅማውን ስትጠብቅ ዕድገቱን የጨረሰው የደብረ
ዘይቱ ሊተኛና ፍሬው ሊረግፍ ይችላል ” ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጡት ።
ይህ ሁሉ ሲሆኑ ዮናታን ምንም ሳይተነፍሱ ዐይናቸውን ከአንዷ ቆርቆሮ ተክል ላይ እንደ ተከሉ ቀርተው ነበር
እያንዳንዱ ቆርቆሮ የያዘው ስምንት ፍሬ ነው ፤ የዮናታንን ዐይን የጠለፈች ቆርቆሮ ሰባቱን ፍሬዎች ጅፍ አርጋ አብቅላ አንዷን አቅጭጫ አስቀርታለች ። ዮናታን በመቀጨጭ ላይ ያለችውን የስንዴ ዘለላ አትኩረው ሲመለከቱ አቤል በሃሳባቸው መጣባቸው ስለዚህ ነበር ከአስተያየት ተቆጥበው የቆዩት አቤል እራሱ እንደ ስንዴዋ ዘለላ በመቀጨጭ ላይ ያለ ሎጋ ወጣት ነው አሉ በልባቸው።
ትንሽ ቆይተው ፡ “ ይህችን ነገር ታያታለህ ? ” አሉ ፊታቸውን ወደ ዶክተር አጥናፉ መልሰው ።
የቷን ? ”
አስጎብኝዉም “ ምን ተገኘ ? ” በሚል ስሜት ወደ ቆርቆሮ አተኮረ ።
💥ይቀጥላል💥
ይህ የየት አገር ዐፈር ነው ? ” አሉ ዶክተር አጥናፉ፡ ዐፈሩ በደንብ ተስማምቶአቸው ከሁሉም ፋፍተው የበቀሉትን ዐምስት ያህል የቆርቆሮ ተክሎች እየተመለከቱ
የደብረ ዘይት ዐፊር ነው ” አለ አስጎብኝው ቆርቆሮው ላይ የጻፈውን ኮድ ተመልክቶ ፣ “ ይገርምዎታል ! በአገራችን
የስነንዴ ተክል ርዝመት ውስጥ ከፍተኛውን ደረጃ ሳይዝ አይቀርም ” ብሎ ፥ የዕድገቱን ፍጥነትና ርዝመት
የላከበትን ሰነድ ፍለጋ ማኅደሩን ያገላብጥ ጀመር ።
ፎቶግራፍ አስነሥተኸዋል ? ”
“አላነሳሁትም ። የጅማው ዐፈር ላይ የተተከሉት ፍጥነትም ባይኖራቸው ዕድገታቸውን ስላላቋረጡ ትንሽ
ልጠብቃቸውና ኣንድ ላይ አስነሣቸዋለሁ ብየ ነው ” አለ አስጎውብኝ ፥ ፊተ ብቻ ሳይሆን ልቡም ፈክቶ የፎቶግራፍ
ጥያቄ ለፕሮጄክቱ ፍጻሜ መቃረቢያ ስለሆነ ዶክተር አጥናፉ ይህን ማንሣታቸው በተዘዋዋሪም ሆን በውበቱ እንደረኩ ለመገመት አስችሎታል ።
“ አሁኑኑ ብታስነሣው የሚሻል ይመስለኛል ። ካለበለዚያ የጅማውን ስትጠብቅ ዕድገቱን የጨረሰው የደብረ
ዘይቱ ሊተኛና ፍሬው ሊረግፍ ይችላል ” ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጡት ።
ይህ ሁሉ ሲሆኑ ዮናታን ምንም ሳይተነፍሱ ዐይናቸውን ከአንዷ ቆርቆሮ ተክል ላይ እንደ ተከሉ ቀርተው ነበር
እያንዳንዱ ቆርቆሮ የያዘው ስምንት ፍሬ ነው ፤ የዮናታንን ዐይን የጠለፈች ቆርቆሮ ሰባቱን ፍሬዎች ጅፍ አርጋ አብቅላ አንዷን አቅጭጫ አስቀርታለች ። ዮናታን በመቀጨጭ ላይ ያለችውን የስንዴ ዘለላ አትኩረው ሲመለከቱ አቤል በሃሳባቸው መጣባቸው ስለዚህ ነበር ከአስተያየት ተቆጥበው የቆዩት አቤል እራሱ እንደ ስንዴዋ ዘለላ በመቀጨጭ ላይ ያለ ሎጋ ወጣት ነው አሉ በልባቸው።
ትንሽ ቆይተው ፡ “ ይህችን ነገር ታያታለህ ? ” አሉ ፊታቸውን ወደ ዶክተር አጥናፉ መልሰው ።
የቷን ? ”
አስጎብኝዉም “ ምን ተገኘ ? ” በሚል ስሜት ወደ ቆርቆሮ አተኮረ ።
💥ይቀጥላል💥
#የታካሚው_ማስታወሻ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
#ምዱካን_ስወራ
ለመሞት ወስኛለሁ፡፡ ግን፣ ደስተኛ የምመስላቸው ቤተሰቦቼ፣ስኬታማ እንደሆንኩ፣ በደስታ እየኖርኩ እንዳለሁ እያሰቡ እንዲቀሩ፣በጥንቃቄ ዱካዬን አጥፍቼ ነው መሞት ያለብኝ፡፡ ልክ ከህይወታችን፣ቀስ በቀስ ጠፍተው እንደተረሱ ሰዎች፣ የት እንዳሉ ምን እንደሆኑ ትዝ እንደማይሉን ሰዎች፣ ዝም፣ ጭጭ፣ ጭልጥ ብዬ መቅረት ነው
ያለብኝ::ጥሩ ደብዛ ማጥፊያ የት ይሆን የሚገኘው? የት ነው አስክሬኔ ወድቆ
ሲገኝ፣ እንደቀልድ ሳይመረመር፣ ማነው? ከየት ነው? ሳይባል ሊቀበር ሚችለው? የት ሊሆን ይችላል?
ገቢና ወጪ ሰው የሚበዛባቸው ከተሞች፣ አዲስ ሰው፣ ፀጉረ ልውጥ ሰው፣ ማነው? ከየት ነው? መቼ መጣ? ለምን መጣ? ተብሎ ትኩረት ማይስብባቸው ከተማዎች፡፡ የድንበር ከተሞች ናቸው፡፡ በየቀኑ አዳዲስ ሰዎች ሚገቡ፣ ሚወጡባቸው፡፡ ከሀገር የሚወጣ፣ የሚሰደድ የሚሰባሰቡባቸው፡፡ ኮንትሮባንድ ነጋዴዎች ሚርመሰመሱባቸው፡፡ከነዋሪው በላይ፣ መጪና ሂያጁ ሚበዛባቸው ከተሞች፡፡ እዛነው፣ ሰው እንደዘበት ሚቀበርበት፡፡ ህይወት እርካሽ የሆነበት፡፡ አስክሬን እንደቀልድ አፈር ማስ ማስ ተደርጎ፣ ሚቀበርበት፡፡ አዎ! ወደ እዛ ሄጄ እራሴን
ማጥፋት አለብኝ፡፡
የትኛው የድንበር ከተማ ይሻለኛል? ሞያሌ? መተማ? ሑመራ? አንዳቸውንም ሄጄባቸዋው አላውቅም፡፡ የቱን ልምረጥ? ለምን እንደሆነ ባላውቅም፣ ወደ መተማ መሄድ የተሻለ መስሎ ተሰማኝ፡፡ እዛ ሄጄ፣
እኔነቴን የሚገልፅ መረጃዎቼን ካጠፋሁ በኋላ፣ ሀገራቸውን ተሰናብተው
እንደሚሄዱ ሰዎች፣ እኔም ተሰናብቼ እሄዳለሁ፡፡ እነሱ ይመለሱ ይሆናል፣ እኔ ግን አልመለስም፡፡ እስከ ወዲያኛው እችን አሰልቺና አታካች አለም እሰናበታታለሁ፡፡
በነጋታው ረፋዱ አምስት ሰዓት አካባቢ፣ ከአዲስ አበባ ጎጃም በረንዳ ወደ ማርቆስ የሚሄድ አባዱላ ተሳፈርኩ፡፡ ከኋላ ወንበር አንድ የቀረው መቀመጫ ባዶ ነው፡፡ ተቀመጥኩ፡፡ ባህርዳር፣ ደ/ማርቆስ
ወያላው ይጣራል፡፡ እንደተቀመጥኩ ሞባይሌን አውጥቼ፣ የተለመደ
ፌስቡኬን መበርበር ጀመርኩኝ፡፡ እያነበብኩ ላይክና ኮሜንት አደርጋለሁ፡፡ በዚህም ሁኔታዎች ውስጥ ሆኜ፣ በማነበው ነገር ቅፅበታዊ ንዴትና ደስታ ይሰማኛል፡፡ የማወቅ ፍላጎቴም እንደዛው አለ፡፡ ዓለምን ተጠይፌ፣ ስለ ዓለም ለማወቅ ስልኬን እበረብራለሁ፡፡ ምን አይነት ግራ ነገር ነው፡፡ 'ማምሻም እድሜ ነው፣ ሆኖብኝ ይሆን፡፡ ድንገት፣ “እዚህ
ጋር ሰው አለ?” የሚል ድምፅ ተሰማኝ፡፡ ቀና አላልኩም፡፡ ጭንቅላቴን
በመወዝወዝ የለም የሚል ምልክት ሰጠሁ፡፡
የማነበው ነገር ትኩረቴን ስቦታል፡፡ ፌስቡክ የሀገራችንን የፖለቲካ መዘወሪያ መስሏል፡፡ ሰው ሁሉ ፖለቲከኛና አክቲቪስት ሆኗል፡፡ ሀገሪቷ የሚያስፈልጋት ሙያ ጋዜጠኛና ፖለቲከኛ እንደሆነ፣ ሁሉም ሙያውን ትቶ ተመራጭ ጋዜጠኛ፣ የፖለቲካ ተንታኝና
አክቲቪስት ለመሆን ይታትራሉ፡፡ ምን እየሆንን ነው?፣ ፖለቲከኛ ባልሆንም እንደመረጃ ስለዓለም ጉዳይ ባገኘሁት አጋጣሚ እከታተላለሁ፡፡ሶሻል ሚዲያ አላማው የተሻለ ተጠያቂነትና ዲሞክራሲ መገንባትና ማስፈን እንደሆነ እሰማለሁ፡፡ በጣም ጠቃሚ ፈጠራም እንደሆነ ግልፅ
ነው፡፡ ግን የተሻለ ቁጥጥር ሚፈልግ ይመስለኛል፡፡ ሶሻል ሚዲያ በዓለማችን ከተስፋፋ በኋላ፣ ዓለማችን ይበልጥ በቀውስ የተሞላች ይመስለኛል፡፡ ከቱኒዚያ የተነሳው የአረብ አብዮት፣ ሊቢያ፣ ግብፅ፣ የመን እያለ ሀገራችን ገብቷል፡፡ አሁን አሁን ሳስበው አሜሪካንና ዌስተርኖች በእርዳታና በሌላ ዲፕሎማቲክ ጫና ያስፈጽሙት የነበረው የአንጋሽነት “King Maker” ሚና ሀገራቶች ከቻይና ጋር በመተባበር በቀላሉ
አልጠመዘዝ ሲሏቸው ያመጡት አማራጭ ይመስለኛል፡፡
በእርግጥ አሁን አሁን፣ አሜሪካንም ሆነ አውሮፓውያን በአፍሪካም ሆነ በሌሎች አህጉራት ስላሉ ታዳጊ ሀገራት እድገትና
ዴሞክራሲ ይጨነቃሉ ብዬ ማመን እየከበደኝ ነው፡፡ ሀያላን ሀገራቱ፣
ዋናው የሚያስጨንቃቸው የራሳቸው ሀገራት ቋሚ ጥቅምን ማረጋጥ
ይመስላል፡፡ በሊቢያ፣ በኢራቅ፣ በየመንና በሶሪያ የተከሰተውን በዓለም
ታሪክ ታይቶ ማይታወቅ የሰበአዊ ቀውሶችን አይተው እንዳላየ መሆናቸው፣ እነዚህ ሀያላን ሀገራት አላማችን፣ ዓለምን ለሰው ልጆች ሁሉ ለኑሮ የተመቸች ማድረግ ነው' የሚለው ዲስኩር፣ ለሽፋንነት የሚደረግ ባዶ ሽንገላ እንደሆነ እንድናስብ ያስገድዳል፡፡
እንደዚህ እያሰብኩ መኪናችን ሞልቶ፣ መንገድ ጀምረን፣እንጦጦ ኬላ ለፍተሻ እንድንወርድ ታዘዝን፡፡ ከሄድኩበት ሃሳብ ባነንኩ፡፡ፍተሻውን ጨርሰን ወደ መኪናችን ተመልሰን ገባን፡፡እኔ የተቀመጥኩት
ወንበር ላይ አንዲት ቆንጅዬ ልጅ ተቀምጣለች፡፡ እግሯን ዘወር አድርጋ፣
ወደቦታዬ እንድገባ አሳለፈችኝ፡፡ ቅድም “እዚህ ጋር ሰው አለው?” ያለችኝ
እርሷ ነበረች፡፡ ቀይ፣ ወጣት፣ ቆንጆ ነች፡፡ ሰሞኑን፣ በህይወቴ የመጣብኝ
ምስቅልቅሎሽ ከሴቶች ጋር በተያያዘ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ሴቶች
መጥፊያዬ ናቸው ብያለሁ፡፡ላልደርስባቸው ምያለሁ፡፡ አሁን ሰይጣን
በዚህች የቀይ ቆንጆ ሊፈትነኝ አጠገቤ አስቀምጧታል፡፡ አላደርገውም ብዬ ስልኬን መበርበሬን ቀጠልኩ፡፡ የፌስ ቡክ ወሬ እንደቅድሙ አልጥም አለኝ፡፡ ሃሳቤ ከእርሷ አልወጣ አለ፡፡ የሚሞት ሰው ይፈራል እንዴ?፣ባክህ ዝም ብለህ እድልህን ሞክር ይለኛል ውስጤ፡፡ የስልኬን ዳታ አጠፋሁት፡፡ እንደሚያድን ነብር፣ ሁሉ ነገሬን ወደ እርሷ ቀሰርኩ።
በደንብ ተመለከትኳት፡፡ ጅንስ ሱሪና ኮት ለብሳለች፡፡ እድሜዋ ቢበዛ ሃያዎቹ መጀመሪያ ቢሆን ነው፡፡ ለመተዋወቅ ወሰንኩ፡፡ እንዴት ልጀምር እያልኩ ሳስብ፣ ታፋዎቿ ላይ መፅሀፍ አየሁ፡፡ ታፋዋን ጎሸም አደረኩና፣
“ልየው?” አልኳት፣ እጄን ወደ መፅሐፉ እየጠቆምኩ፡፡
ይቻላል በሚል ጭንቅላቷን ነቀነቀችልኝ፡፡ መፅሀፉን አነሳሁት::የፊት ገፅ ሽፋኑ ላይ ጓድ ኮርኔል መንግስቱ ኃ/ማርያም ወታደራዊ ዩኒፎርም ለብሰው የተነሱት ፎቶ ይታያል፡፡ የመፅሀፉ ርዕስ ነበር
ይላል፡፡ በጣም ገረመኝ፡፡ ይህን መፅሀፍ ብዙ ጊዜ መፅሐፍ አዟሪዎች ላይ አይቼዋለሁ፡፡ አንስቼ የጀርባ ፅሁፉን ለማንበብ እንኳ ተነሳሽነቱ አልነበረኝም፡፡ የዛ ትውልድን መፅሐፍት ፈልጌ ነበር የማነበው።ይገርሙኛል፤ ያስቀኑኛል፤ ይደንቁኛልም፡፡ በመንግስት አፍንጫ ስር
የመደራጀት ጥበባቸው፣ ዲሲፕሊናቸው፣ ለድርጅታቸው ያላቸው ፍፁማዊ ታማኝነት፣ ይደንቀኛል፡፡ ስለዚህ፣ ፈልጌ አነባቸዋለሁ።የመንግስቱ ኃ/ማርያምን ጨፍጫፊነትን ይቅር የምልበት ምክንያት
ፍለጋ ግን አላነብም፡፡ ልቤ ዝግ ነው፡፡ ስለዚህ አልገዛሁትም፡፡ እንኳን መፅሐፉን ገዝቼ ላነበው፣ ሚያነበው ሰው ያለ ፀአይመስለኝም ነበር፡፡
“ያንቺ ነው?” አልኳት ተገርሜ፡፡
“አሁን አይደል ከኔ የወሰድከው?” አለችኝ፣ በፈገግታ ነጫጭ ጥርሶቿን ፍልቅቅ አድርጋ፡፡ ፈገግታዋ የልብን ምት የሚጨምር ጨረር ይረጫል፡፡
“ማለቴ ልታነቢው ነው?” በመገረም ጠየኳት፡፡
“እንዴ...! አዎ! ምነው? ችግር አለው?”
ደግማ ፈገግ እያለች፡፡
“ኢሰፓ ቤተሰብ አለሽ?”
“ኧረ የለኝም፡፡” ኪ.ኪ.ኪ...
“ግን፣ ለምን እንዲህ አልከኝ?”
“ሴት፣ የፖለቲካ መፅሀፍ፣ ደግሞ የመንስቱ ኃ/ማርያም ታሪክ፣ በጣም ደንቆኝ ነው!”
“መፅሐፉን አንብበኸዋል ግን?”
“ኧረ በጭራሽ! ሳየው ገና ያንገሸግሸኛል!”
“ብታነበው ግን፣ እርግጠኛ ነኝ እንደዚህ አትጠላውም፡፡”
“ምን ፈልጌ ነው ማነበው?
አልጨፈጨፍኩም እንዲለኝ? ወይስ
ቀይ ሽብር ፅድቅ ነው እንዲለኝ? ለማንኛውም ተይው፡፡ ወዴት ነሽ?”
“ባህርዳር፡፡ አንተስ?”
“ባህር ዳር፣ ከዛ ጎንደር
፡
፡
#ክፍል_ሀያ
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
#ምዱካን_ስወራ
ለመሞት ወስኛለሁ፡፡ ግን፣ ደስተኛ የምመስላቸው ቤተሰቦቼ፣ስኬታማ እንደሆንኩ፣ በደስታ እየኖርኩ እንዳለሁ እያሰቡ እንዲቀሩ፣በጥንቃቄ ዱካዬን አጥፍቼ ነው መሞት ያለብኝ፡፡ ልክ ከህይወታችን፣ቀስ በቀስ ጠፍተው እንደተረሱ ሰዎች፣ የት እንዳሉ ምን እንደሆኑ ትዝ እንደማይሉን ሰዎች፣ ዝም፣ ጭጭ፣ ጭልጥ ብዬ መቅረት ነው
ያለብኝ::ጥሩ ደብዛ ማጥፊያ የት ይሆን የሚገኘው? የት ነው አስክሬኔ ወድቆ
ሲገኝ፣ እንደቀልድ ሳይመረመር፣ ማነው? ከየት ነው? ሳይባል ሊቀበር ሚችለው? የት ሊሆን ይችላል?
ገቢና ወጪ ሰው የሚበዛባቸው ከተሞች፣ አዲስ ሰው፣ ፀጉረ ልውጥ ሰው፣ ማነው? ከየት ነው? መቼ መጣ? ለምን መጣ? ተብሎ ትኩረት ማይስብባቸው ከተማዎች፡፡ የድንበር ከተሞች ናቸው፡፡ በየቀኑ አዳዲስ ሰዎች ሚገቡ፣ ሚወጡባቸው፡፡ ከሀገር የሚወጣ፣ የሚሰደድ የሚሰባሰቡባቸው፡፡ ኮንትሮባንድ ነጋዴዎች ሚርመሰመሱባቸው፡፡ከነዋሪው በላይ፣ መጪና ሂያጁ ሚበዛባቸው ከተሞች፡፡ እዛነው፣ ሰው እንደዘበት ሚቀበርበት፡፡ ህይወት እርካሽ የሆነበት፡፡ አስክሬን እንደቀልድ አፈር ማስ ማስ ተደርጎ፣ ሚቀበርበት፡፡ አዎ! ወደ እዛ ሄጄ እራሴን
ማጥፋት አለብኝ፡፡
የትኛው የድንበር ከተማ ይሻለኛል? ሞያሌ? መተማ? ሑመራ? አንዳቸውንም ሄጄባቸዋው አላውቅም፡፡ የቱን ልምረጥ? ለምን እንደሆነ ባላውቅም፣ ወደ መተማ መሄድ የተሻለ መስሎ ተሰማኝ፡፡ እዛ ሄጄ፣
እኔነቴን የሚገልፅ መረጃዎቼን ካጠፋሁ በኋላ፣ ሀገራቸውን ተሰናብተው
እንደሚሄዱ ሰዎች፣ እኔም ተሰናብቼ እሄዳለሁ፡፡ እነሱ ይመለሱ ይሆናል፣ እኔ ግን አልመለስም፡፡ እስከ ወዲያኛው እችን አሰልቺና አታካች አለም እሰናበታታለሁ፡፡
በነጋታው ረፋዱ አምስት ሰዓት አካባቢ፣ ከአዲስ አበባ ጎጃም በረንዳ ወደ ማርቆስ የሚሄድ አባዱላ ተሳፈርኩ፡፡ ከኋላ ወንበር አንድ የቀረው መቀመጫ ባዶ ነው፡፡ ተቀመጥኩ፡፡ ባህርዳር፣ ደ/ማርቆስ
ወያላው ይጣራል፡፡ እንደተቀመጥኩ ሞባይሌን አውጥቼ፣ የተለመደ
ፌስቡኬን መበርበር ጀመርኩኝ፡፡ እያነበብኩ ላይክና ኮሜንት አደርጋለሁ፡፡ በዚህም ሁኔታዎች ውስጥ ሆኜ፣ በማነበው ነገር ቅፅበታዊ ንዴትና ደስታ ይሰማኛል፡፡ የማወቅ ፍላጎቴም እንደዛው አለ፡፡ ዓለምን ተጠይፌ፣ ስለ ዓለም ለማወቅ ስልኬን እበረብራለሁ፡፡ ምን አይነት ግራ ነገር ነው፡፡ 'ማምሻም እድሜ ነው፣ ሆኖብኝ ይሆን፡፡ ድንገት፣ “እዚህ
ጋር ሰው አለ?” የሚል ድምፅ ተሰማኝ፡፡ ቀና አላልኩም፡፡ ጭንቅላቴን
በመወዝወዝ የለም የሚል ምልክት ሰጠሁ፡፡
የማነበው ነገር ትኩረቴን ስቦታል፡፡ ፌስቡክ የሀገራችንን የፖለቲካ መዘወሪያ መስሏል፡፡ ሰው ሁሉ ፖለቲከኛና አክቲቪስት ሆኗል፡፡ ሀገሪቷ የሚያስፈልጋት ሙያ ጋዜጠኛና ፖለቲከኛ እንደሆነ፣ ሁሉም ሙያውን ትቶ ተመራጭ ጋዜጠኛ፣ የፖለቲካ ተንታኝና
አክቲቪስት ለመሆን ይታትራሉ፡፡ ምን እየሆንን ነው?፣ ፖለቲከኛ ባልሆንም እንደመረጃ ስለዓለም ጉዳይ ባገኘሁት አጋጣሚ እከታተላለሁ፡፡ሶሻል ሚዲያ አላማው የተሻለ ተጠያቂነትና ዲሞክራሲ መገንባትና ማስፈን እንደሆነ እሰማለሁ፡፡ በጣም ጠቃሚ ፈጠራም እንደሆነ ግልፅ
ነው፡፡ ግን የተሻለ ቁጥጥር ሚፈልግ ይመስለኛል፡፡ ሶሻል ሚዲያ በዓለማችን ከተስፋፋ በኋላ፣ ዓለማችን ይበልጥ በቀውስ የተሞላች ይመስለኛል፡፡ ከቱኒዚያ የተነሳው የአረብ አብዮት፣ ሊቢያ፣ ግብፅ፣ የመን እያለ ሀገራችን ገብቷል፡፡ አሁን አሁን ሳስበው አሜሪካንና ዌስተርኖች በእርዳታና በሌላ ዲፕሎማቲክ ጫና ያስፈጽሙት የነበረው የአንጋሽነት “King Maker” ሚና ሀገራቶች ከቻይና ጋር በመተባበር በቀላሉ
አልጠመዘዝ ሲሏቸው ያመጡት አማራጭ ይመስለኛል፡፡
በእርግጥ አሁን አሁን፣ አሜሪካንም ሆነ አውሮፓውያን በአፍሪካም ሆነ በሌሎች አህጉራት ስላሉ ታዳጊ ሀገራት እድገትና
ዴሞክራሲ ይጨነቃሉ ብዬ ማመን እየከበደኝ ነው፡፡ ሀያላን ሀገራቱ፣
ዋናው የሚያስጨንቃቸው የራሳቸው ሀገራት ቋሚ ጥቅምን ማረጋጥ
ይመስላል፡፡ በሊቢያ፣ በኢራቅ፣ በየመንና በሶሪያ የተከሰተውን በዓለም
ታሪክ ታይቶ ማይታወቅ የሰበአዊ ቀውሶችን አይተው እንዳላየ መሆናቸው፣ እነዚህ ሀያላን ሀገራት አላማችን፣ ዓለምን ለሰው ልጆች ሁሉ ለኑሮ የተመቸች ማድረግ ነው' የሚለው ዲስኩር፣ ለሽፋንነት የሚደረግ ባዶ ሽንገላ እንደሆነ እንድናስብ ያስገድዳል፡፡
እንደዚህ እያሰብኩ መኪናችን ሞልቶ፣ መንገድ ጀምረን፣እንጦጦ ኬላ ለፍተሻ እንድንወርድ ታዘዝን፡፡ ከሄድኩበት ሃሳብ ባነንኩ፡፡ፍተሻውን ጨርሰን ወደ መኪናችን ተመልሰን ገባን፡፡እኔ የተቀመጥኩት
ወንበር ላይ አንዲት ቆንጅዬ ልጅ ተቀምጣለች፡፡ እግሯን ዘወር አድርጋ፣
ወደቦታዬ እንድገባ አሳለፈችኝ፡፡ ቅድም “እዚህ ጋር ሰው አለው?” ያለችኝ
እርሷ ነበረች፡፡ ቀይ፣ ወጣት፣ ቆንጆ ነች፡፡ ሰሞኑን፣ በህይወቴ የመጣብኝ
ምስቅልቅሎሽ ከሴቶች ጋር በተያያዘ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ሴቶች
መጥፊያዬ ናቸው ብያለሁ፡፡ላልደርስባቸው ምያለሁ፡፡ አሁን ሰይጣን
በዚህች የቀይ ቆንጆ ሊፈትነኝ አጠገቤ አስቀምጧታል፡፡ አላደርገውም ብዬ ስልኬን መበርበሬን ቀጠልኩ፡፡ የፌስ ቡክ ወሬ እንደቅድሙ አልጥም አለኝ፡፡ ሃሳቤ ከእርሷ አልወጣ አለ፡፡ የሚሞት ሰው ይፈራል እንዴ?፣ባክህ ዝም ብለህ እድልህን ሞክር ይለኛል ውስጤ፡፡ የስልኬን ዳታ አጠፋሁት፡፡ እንደሚያድን ነብር፣ ሁሉ ነገሬን ወደ እርሷ ቀሰርኩ።
በደንብ ተመለከትኳት፡፡ ጅንስ ሱሪና ኮት ለብሳለች፡፡ እድሜዋ ቢበዛ ሃያዎቹ መጀመሪያ ቢሆን ነው፡፡ ለመተዋወቅ ወሰንኩ፡፡ እንዴት ልጀምር እያልኩ ሳስብ፣ ታፋዎቿ ላይ መፅሀፍ አየሁ፡፡ ታፋዋን ጎሸም አደረኩና፣
“ልየው?” አልኳት፣ እጄን ወደ መፅሐፉ እየጠቆምኩ፡፡
ይቻላል በሚል ጭንቅላቷን ነቀነቀችልኝ፡፡ መፅሀፉን አነሳሁት::የፊት ገፅ ሽፋኑ ላይ ጓድ ኮርኔል መንግስቱ ኃ/ማርያም ወታደራዊ ዩኒፎርም ለብሰው የተነሱት ፎቶ ይታያል፡፡ የመፅሀፉ ርዕስ ነበር
ይላል፡፡ በጣም ገረመኝ፡፡ ይህን መፅሀፍ ብዙ ጊዜ መፅሐፍ አዟሪዎች ላይ አይቼዋለሁ፡፡ አንስቼ የጀርባ ፅሁፉን ለማንበብ እንኳ ተነሳሽነቱ አልነበረኝም፡፡ የዛ ትውልድን መፅሐፍት ፈልጌ ነበር የማነበው።ይገርሙኛል፤ ያስቀኑኛል፤ ይደንቁኛልም፡፡ በመንግስት አፍንጫ ስር
የመደራጀት ጥበባቸው፣ ዲሲፕሊናቸው፣ ለድርጅታቸው ያላቸው ፍፁማዊ ታማኝነት፣ ይደንቀኛል፡፡ ስለዚህ፣ ፈልጌ አነባቸዋለሁ።የመንግስቱ ኃ/ማርያምን ጨፍጫፊነትን ይቅር የምልበት ምክንያት
ፍለጋ ግን አላነብም፡፡ ልቤ ዝግ ነው፡፡ ስለዚህ አልገዛሁትም፡፡ እንኳን መፅሐፉን ገዝቼ ላነበው፣ ሚያነበው ሰው ያለ ፀአይመስለኝም ነበር፡፡
“ያንቺ ነው?” አልኳት ተገርሜ፡፡
“አሁን አይደል ከኔ የወሰድከው?” አለችኝ፣ በፈገግታ ነጫጭ ጥርሶቿን ፍልቅቅ አድርጋ፡፡ ፈገግታዋ የልብን ምት የሚጨምር ጨረር ይረጫል፡፡
“ማለቴ ልታነቢው ነው?” በመገረም ጠየኳት፡፡
“እንዴ...! አዎ! ምነው? ችግር አለው?”
ደግማ ፈገግ እያለች፡፡
“ኢሰፓ ቤተሰብ አለሽ?”
“ኧረ የለኝም፡፡” ኪ.ኪ.ኪ...
“ግን፣ ለምን እንዲህ አልከኝ?”
“ሴት፣ የፖለቲካ መፅሀፍ፣ ደግሞ የመንስቱ ኃ/ማርያም ታሪክ፣ በጣም ደንቆኝ ነው!”
“መፅሐፉን አንብበኸዋል ግን?”
“ኧረ በጭራሽ! ሳየው ገና ያንገሸግሸኛል!”
“ብታነበው ግን፣ እርግጠኛ ነኝ እንደዚህ አትጠላውም፡፡”
“ምን ፈልጌ ነው ማነበው?
አልጨፈጨፍኩም እንዲለኝ? ወይስ
ቀይ ሽብር ፅድቅ ነው እንዲለኝ? ለማንኛውም ተይው፡፡ ወዴት ነሽ?”
“ባህርዳር፡፡ አንተስ?”
“ባህር ዳር፣ ከዛ ጎንደር
👍3❤2
“ለስራ ነው?
“አይ እንዲሁ አገር ለማየት፡፡”
“ሀበሻ ቱሪስት ነሀ?”
“ሳይሆን እረፍት ስሆን፣ ጃምቦ ስጠጣ ከመክረም፣ መዞር እወዳለሁ፡፡”
“ጥሩ ልምድ ነው፡፡”
“አንቺስ፣ ለስራ ነው?”
“አይ ወደ ቤተሰብ፣ ወንድሜ ጋር እየሄድኩ ነው፡፡”የባጥ የቆጡን እያወራን፣ ገብረጉራቻ ደርሰን ለምሳ ቆምን፡፡
አብረን ምሳ በላን፡፡ ቡና ጠጣን፡፡ ቶሎ ተላምደናል፡፡ እየተላፋችኝ ማውራት ጀምራለች፡፡ ከምሳ ስንመለስ፣ ወሬ እያለቀብን መጣ፡፡ የወሬ ርዕስ ለመፈለግ ያክል፣ የያዘችውን መፅሀፍ ተቀበልኳትና ማንበብ ጀመርኩ ::
“በኢትዮጵያ የተደረገው የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ህዝብን አስቆጣ፤ ተማሪዎች በሰልፍ ጎዳናዎችን ሞሏቸው። ዩኒቨርስቲዎች ተዘጉ፣ ይሄ ሁሉ አመፅና አብዮት አንድ አጭር፣ ቀጭንና ጥቁር ሰው ወደ ስልጣን እያመጣ እንደነበር ግን ማንም አልገመተም ነበር፡፡ አፄው፣ በመንግስቱ ኃ/ማርያም ተተኩ፡፡” መፅሀፉ ከፍተኛ የመሳብ ሀይል አለው፡፡ አጠገቤ
ከተቀመጠችው፣ ላጠምዳት መረቤን ከዘረጋሁባት ውብ በላይ፣ ስቦ ወደራሱ አሰመጠኝ፡፡ ለወሬ መጀመሪያነት የከፈትኩት መፅሀፍ፣ ሳላስበው ዋጠኝ፡፡ እርሷን እስክረሳት ድረስ አስመጠኝ፡፡ የመፅሀፉ ኪነጥበባዊ ደረጃና የመረጃዎቹ ፍሰት፣ ከሽፋን ገፁ እጅግ የላቁ ሆነው አገኘኋቸው፡፡ እጅግ ምርጥ መፅሀፍ ነው፡፡
ድንገት አጠገቤ ያለችው ቆንጆ ልጅ ትከሻዬን ደገፍ አለችብኝ፡፡ድንገጥ ብዬ አየኋት፡፡ ለመተኛት እየተመቻቸች ነው፡፡ የት እንደደረስን፣ ቀና ብዬ በመኪናው መስኮት ወደ ውጭ ተመለከትኩ፤ አባይ በረሃ ገብተናል፡፡ አይፈረድባትም፤ የበረሀው ሙቀት እንቅልፍ ይጫጫናል፡፡
እኔ ግን፣ ለብዙ ጊዜ በጠላሁት መፅሀፍ ተመስጫለሁ፡፡ ሁለት ምዕራፎችን እንደዘበት ወጣኋቸው፡፡ ግሩም መፅሀፍ ነው፡፡ ስለመፅሀፉ ተሳስቻለሁ፡፡እስከዛሬም ደጋግሜ ላነበው ይገባ ነበር፡፡ የአባይ በርሀ መንገድ ይጥመዘመዛል፡፡ መኪናው ከግራ ወደቀኝ ያላጋናል፡፡ ወደ
ዝቅተኛው ቦታ እየቀረብን ስንመጣ፣ ሙቀቱ ጨምረ፡፡ ልጅቷ ከትከሻዬ
ላይ ተንሸራታ፣ታፋዎቼ ላይ ተመቻችታ ተኛች፡፡
አሁን፣ የአባይ ወንዝ በደንብ ይታየን ጀመር፡፡ መፅሀፉን አጥፌ ትኩረቴን አባይ ላይ አደረኩ፡፡ አባይ የአገር ፍቅር የአገር ሲሳይ...፣
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
“አይ እንዲሁ አገር ለማየት፡፡”
“ሀበሻ ቱሪስት ነሀ?”
“ሳይሆን እረፍት ስሆን፣ ጃምቦ ስጠጣ ከመክረም፣ መዞር እወዳለሁ፡፡”
“ጥሩ ልምድ ነው፡፡”
“አንቺስ፣ ለስራ ነው?”
“አይ ወደ ቤተሰብ፣ ወንድሜ ጋር እየሄድኩ ነው፡፡”የባጥ የቆጡን እያወራን፣ ገብረጉራቻ ደርሰን ለምሳ ቆምን፡፡
አብረን ምሳ በላን፡፡ ቡና ጠጣን፡፡ ቶሎ ተላምደናል፡፡ እየተላፋችኝ ማውራት ጀምራለች፡፡ ከምሳ ስንመለስ፣ ወሬ እያለቀብን መጣ፡፡ የወሬ ርዕስ ለመፈለግ ያክል፣ የያዘችውን መፅሀፍ ተቀበልኳትና ማንበብ ጀመርኩ ::
“በኢትዮጵያ የተደረገው የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ህዝብን አስቆጣ፤ ተማሪዎች በሰልፍ ጎዳናዎችን ሞሏቸው። ዩኒቨርስቲዎች ተዘጉ፣ ይሄ ሁሉ አመፅና አብዮት አንድ አጭር፣ ቀጭንና ጥቁር ሰው ወደ ስልጣን እያመጣ እንደነበር ግን ማንም አልገመተም ነበር፡፡ አፄው፣ በመንግስቱ ኃ/ማርያም ተተኩ፡፡” መፅሀፉ ከፍተኛ የመሳብ ሀይል አለው፡፡ አጠገቤ
ከተቀመጠችው፣ ላጠምዳት መረቤን ከዘረጋሁባት ውብ በላይ፣ ስቦ ወደራሱ አሰመጠኝ፡፡ ለወሬ መጀመሪያነት የከፈትኩት መፅሀፍ፣ ሳላስበው ዋጠኝ፡፡ እርሷን እስክረሳት ድረስ አስመጠኝ፡፡ የመፅሀፉ ኪነጥበባዊ ደረጃና የመረጃዎቹ ፍሰት፣ ከሽፋን ገፁ እጅግ የላቁ ሆነው አገኘኋቸው፡፡ እጅግ ምርጥ መፅሀፍ ነው፡፡
ድንገት አጠገቤ ያለችው ቆንጆ ልጅ ትከሻዬን ደገፍ አለችብኝ፡፡ድንገጥ ብዬ አየኋት፡፡ ለመተኛት እየተመቻቸች ነው፡፡ የት እንደደረስን፣ ቀና ብዬ በመኪናው መስኮት ወደ ውጭ ተመለከትኩ፤ አባይ በረሃ ገብተናል፡፡ አይፈረድባትም፤ የበረሀው ሙቀት እንቅልፍ ይጫጫናል፡፡
እኔ ግን፣ ለብዙ ጊዜ በጠላሁት መፅሀፍ ተመስጫለሁ፡፡ ሁለት ምዕራፎችን እንደዘበት ወጣኋቸው፡፡ ግሩም መፅሀፍ ነው፡፡ ስለመፅሀፉ ተሳስቻለሁ፡፡እስከዛሬም ደጋግሜ ላነበው ይገባ ነበር፡፡ የአባይ በርሀ መንገድ ይጥመዘመዛል፡፡ መኪናው ከግራ ወደቀኝ ያላጋናል፡፡ ወደ
ዝቅተኛው ቦታ እየቀረብን ስንመጣ፣ ሙቀቱ ጨምረ፡፡ ልጅቷ ከትከሻዬ
ላይ ተንሸራታ፣ታፋዎቼ ላይ ተመቻችታ ተኛች፡፡
አሁን፣ የአባይ ወንዝ በደንብ ይታየን ጀመር፡፡ መፅሀፉን አጥፌ ትኩረቴን አባይ ላይ አደረኩ፡፡ አባይ የአገር ፍቅር የአገር ሲሳይ...፣
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1🔥1
#የታካሚው_ማስታወሻ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
አባይ ማደሪያ የለው ግንድ ይዞይዞራል፡፡ ከልጅነቴ ጀምሮ አባይ፣ አባይ ሲባል እየሰማሁ ነው ያደኩት፡፡ በውስጤ አባይ ግዙፍ ነው፡፡ ወደ ድልድዩ እየተጠጋን ነው፡፡ አሁን በደንብ ወንዙ ይታየኛል፡፡ የአለም እረጅሙን ወንዝ አባይ...፣ በሱዳን አቋርጦ፣ ግብፅን አጠጥቶ፣ ተርፎ
ሜድትራያንያን ባህር የሚገባው አባይ... ፣ በሁሉም አቅጣጫ ለማየት ሞከርኩ፣ በደንብ ተንጠራራሁ፣ አባይ እንደጠበኩት ግዙፍ አልሆንልህ አለኝ፡፡ ውስጤ አግዝፌው ስለነበር ይሆን?፣ ወይስ ገና ከዚህ ወዲያ ነው ሚገዝፈው...? ይሄን እንዴት እስከዛሬ ሳንገድብ ቆየን? እነዚህ
ሃሳቦች በውስጤ ተሯሯጡ፡፡
ልጅቷ ነቃች፡፡ ዐይኗን እያሻሸች ቀና ብላ አየችኝ፡፡
“እንቅልፋም!” አልኳት፡፡
ፈገግ ብላ፣ “ብዙ ተኛሁ እንዴ?”
“እንጃ፣ እያነበብኩ ነበር፤ አላስተዋልኩም፡፡”
“መፅሀፉ አሪፍ ነው አይደል?”
“በጣም ምርጥ ነው፡፡ ይቅርታ ተሳስቻለሁ፡፡”
“ችግር የለውም፡፡ እንኳን ተመቸህ፡፡”
“እንደውም አልሰጥሽም፤ ወስጄዋለሁ፤” አልኩኝ ፈገግ ብዬ፡፡
“ችግር የለውም፡፡ ሌላ እገዛለሁ፡፡”
“ዋጋውን ግን፣ በእጥፍ እከፍላሁ::”
“በጭራሽ አይሆንም፡፡ እንደውም ስጦታዬ ነው፡፡”
“እንዴ ለምን?፣ምን አድርጌልሽ?››
«እንደ ፍራሽ ተኝቼብህ ለመጣሁት፡፡”
“ከተማሪማ ስጦታ አልቀበልም፤” አልኩኝ ሆን ብዬ፤ ገና አሁን እንተዋወቅ ላለማለት፡፡
“ማነው ተማሪ ናት ያለህ?”
“ውይ ለካ በደንብ ሳንተዋወቅ ነው፤ ወደ ወሬ የገባነው፡፡ ያቤዝ እባላለሁ።”
“ህይወት፡፡ ስምህ ደስ ሲል፡፡ ምን ማለት ነው?”
“እ...፣ በችግር ውስጥ የተወለደና ለችግሩ መፍትሄ የሆነ ማለት
ነው ሲሉ ሰምቻለው፡፡”
“ትርጉሙም ስሙም በጣም ደስ ይላል፡፡”
“ይሆናል፡፡ እኔ ግን እስካሁን ችግር እንጂ፣ የችግር መፍትሄ ሆኜ አላውቅም፡፡”
“ወደፊት ትሆናለሃ፡፡”
ሃሃሃ...ወደፊት ትሆናለህ'፣ ወደፊቴን ላጠፋው እየሄድኩ እንደሆነ ብታውቂ..፣ በውስጤ አልጎመጎምኩ፡፡ ዳግሞ መፅሀፉን ገለጥኩት፡፡ አላባበለኝም፡፡ በፍጥነት ጭልጥ አድርጎ አስመጠኝ፡፡ ላድናት ጥፍሬን ያሾልኩለት ቆንጅዬ፣ ዳግም አጠገቤ እንደሌለች እረሳኋት፡፡
መልሳ ጋደም አለችብኝ፡፡ አሁን ቤተኛ ሆነናል፡፡ ቀጥታ ታፋዎቼ ላይ ተጋደመች፡፡ ቀይ፣ ለጋና ሰልካካ ፊቷን አየሁት፡፡ ያስጎመዣል፡፡ የሹራብ ጃኬቴን አውልቄ እንድትንተራሰው ሰጠኋት፡፡ ተቀበለችኝ፡፡ መፅሀፉ ግን ማግኔት ነው፡፡ መልሶ ወደ ራሱ ይጎትተኛል፡፡ ወታደሩ የህዝቡን አመፅ እንዴት ወደራሱ ጠምዝዞ እንደቀለበሰው፣ አተራረኩ ይገርማል፡፡ ሻለቃ መንግስቱ በደርጉ ምስረታ ስብሰባ ላይ ባደረገው ዲስኩር፣ እንዴት የሰው
ልብ እንደገዛ ማንበብ ይመስጣል፡፡ የዚያው የመጀምሪያ ቀን ዲስኩር
ማሳረጊያ 'ኢትዮጵያ ትቅደም' መፈክር፣ የሀገሪቷ የአስራ ሰባት ዓመት ቋንቋ መሆኑን ማንበብ ይደንቃል፡፡ አብዛኛውም የሃገራችን ፖለቲካ መዘወሪያ ሃሳቦች እንደዚህ ባሉ ቅፅበታዊና ስሜታዊ ሁኔታ ሚፈጠሩ ይሆን እንዴ ብዬ አሰላሰልኩ፡፡
ህይወት ትገላበጣለች፡፡ ታፋዎቼ መሀል ሞቀኝ፡፡ አሁን ትኩረቴ ሲበተን ታወቀኝ፡፡ የሚሰማኝ ሙቀት፣ ካሰመጠኝ ድንቅ መፅሀፍ፣ እየጎተተ አውጥቶ፣ ትኩረቴን ወደ እርሷ እያደረገው ነው፡፡ ስለእርሷ
ማሰብ ጀመርኩ፡፡ እያነበብኩ፣ አንድ እጄን ጭንቅላቷ ላይ ጣልኩት፡፡
ፀጉሯን መደባበስ ጀመርኩ፡፡ በስሱ ፊቷን ዳበስኩት፡፡ ያፍንጫዋን ስልካካነት ወደታች በስሱ ወረድኩት፣ እናት ልጇን እንደምትዳብሰው፤ ፍቅረኛማቾች እንደሚደባበሱት፣ የከንፈሮቿን ጠርዝ እየተከተልኩ በጣቶቼ ጫፍ ዳበስኳቸው፡፡ ዝም፣ ጭጭ፡፡ መልሼ፣ በፀጉሮቿ መሀል
ጣቶቼን ላኳቸው፡፡ አሁን፣ መፅሀፉን ለይስሙላ ነው የያዝኩት፡፡ እያነበብኩት አይደለም፡፡
ስሜቴ እየሞቀ መጥቷል፡፡ እንቅልፍ ካልወሰዳት፣ የተኛችበት ታፋዎቼ መሀከል ያለው እንቅስቃሴ፣ አፍ አውጥቶ ይናገራል፡፡ አዎ እንቅልፍ ካልወሰዳት፣ እኔ ምንም መናገር አይጠበቅብኝም፡፡ መፅሀፉን ዘግቼ አስቀመጥኩት፡፡ ትኩር ብዬ፣ ቁልቁል እንደ ፍቅረኛ እያየኋት
ነው፡፡ የሌሎች ተሳፋሪዎችን ዐይንና ቀልብ ከሳብን ቆይተናል፡፡ አብረን
የመጣን ፍቅረኛሞች፣ ባልና ሚስት እንጂ፣ በድንገት እዚሁ የተገናኘን
አንመስልም፡፡ ተሳፋሪዎች በአግራሞት እየተመለከቱን ነው፡፡ ህይወት በጣም ቀላል፣ተግባቢና መስህብ ያላት ቆንጆ ነች፡፡ በጣም የምንዋደድ ፍቅረኛሞች እንመስላለን፡፡
ትወስደዋለህ፤ እስጥሃለሁ፤ ያለችኝ ውልብ አለብኝ፡፡ አሁን ለእኔ ጊዜ ስጠኝ መፅሀፉን ሌላ ጊዜ ታነበዋለህ ማለቷ ይሆን? ስሜቴ ሲያድግ ታወቀኝ፡፡ አሁን እንኳን ማንበብ፣ ዐይኔን እንኳ ከእርሷ መንቀል አልቻልኩም፡፡ እዳብሳታለሁ፡፡ እየሰማች ከሆነ፣ ታፋዎቼ መሀከል
የተፈጠረው እሳተ ጎሞራ፣ ስሜቴን በማያወላዳ መልኩ ያሳብቅልኛል፡፡
ማስረዳት አይጠበቅብኝም፡፡ እንቅልፍ እንዳልወስዳት ማረጋገጥ አለብኝ፡፡
ስሜቴን እየሰማችው መሆን አለመሆኑን ማወቅ አለብኝ፡፡ ትኩር ብዬ አየኋት፡፡ ቁልቁል የተንሰለከከ አፍንጫዋን በጣቶቼ በፍቅር እየዳሰስኩት ወረድኩኝ፡፡ ቁልቁል ወርጄ ጫፍ ላይ ስደርስ፣ በጣቶቼ ቀስ ብዬ አፍንጫዋን ጭምቅ፣ እፍን አደረኳት፡፡ ወዲያው ቀና ብላ፣
“ልትገለኝ ነው እንዴ?” አለችኝ፡፡
ፈገግ ብዬ፣ “እና ጥለሽኝ ስትተኚ...”
“አንተስ ጥለኸኝ በመፅሃፉ ስትመሰጥ አልነበር፡፡”
“የእውነት፡፡ መፅሀፉ ውበትሽን ሚገዳደር ነው፡፡”
“ፖለቲካ ትወዳለህ ማለት ነው፡፡”
“እንደዛ ሳይሆን፣ የያ ትውልድ ታሪክ ይማርከኛል፡፡
ችሎታቸው፣ ዲሲፕሊናቸው፣ የሀገር ፍቅራቸው፣ አሁን እንኳን ሀገር እየመሩም እየተቃወሙም ያሉት እነሱ እኮ ናቸው፡፡”
“አሁን ወጣቱ ሁሉ ፖለቲከኛ አይደል እንዴ?”
“ማለቴ፣ አሁን ያለችው ኢትዮጵያ የዛ ትውልድ የአዕምሮ ውጤትና የእጅ ስራ እየሆነችኮ ነው፡፡ ያ ትውልድ መሬት ላራሹ ብሎ ፊውዳሊዝምን በታተነ፡፡ ኢትዮጵያዊ ማነው ብሎ ሞግቶ፣ የብሄር ብሄረሰብን መልክ፣ መልኬ ነው ብላ እምትቀበል ኢትዮጵያን እጇን ጠምዝዞ እየገነባ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የብሄር ብሄረስብ ነች ብለው፣ መሀል አዲስ አበባ ላይ የብሄር ብሄረሰብ አደባባይ አኑረዋል፡፡ ወደድንም ጠላንም
አሻራ ያላቸው ትልቅ ትውልዶች ናቸው፡፡ እኛ በእነሱ ጥላ ተከልለን አሻራ ቢስ ሆነን ልናልፍ ነው፡፡”
“ግን ያ ትውልድ፣ ያልከው ብቻ አይደለም እኮ፡፡ አስተዋዩና ባለ ልዩ አምሮ ያልከው ያ ትውልድ፣ እርስ በርሱ ተባልቷል፡፡ ወንድም ወንድሙን ገሏል፧ ኢትዮጵያዊ ባህል ባልሆነ ጭካኔ ሀገሪቷ የደም
አኬልዳማ አድርጓታል፡፡ ዘጠና ዘጠኝ ከመቶ በላይ አማኝ በሆነ ማሀበረሰብ፣ ከማርክስ ሌኒኒስት አስተምሮ ተነስቶ፣ ሀይማኖት የቀኝ ገዢዎች የማህበረሰብ ማደንዘዣ ድሪቶ ነው፤ አውልቁና ጣሉት አለ፡፡ ማህበረሰቡን እሴት አልባ አደረገው፡፡ መሰረቅ ባህላችን ሆነ፡፡አረ ስንቱን ..::”
“የእርስ በእርስ ጦርነቱን እንኳን ተይው፣ እንደ አንድ የማህበረሰቡ ባህልና እሴት አብሮን የኖረ ነው፡፡ ግን ቆይ ቆይ፣ ሀይማኖት ማህበረሰባችን አላደነዘዘም እያልሽኝ ነው? የሆነ ችግር ሲያጋጥመው
ለመፍታት ከመጣር ይልቅ፣ ሁሉ ለበጎ ነው ብሎ ችግሩን ተላምዶ እንዲኖር ሀይማኖት አላደረገውም እያልሽኝ ነው?”
‹‹ሀይማኖታችን የሚለው ያልሰራ እርሱ አይብላ ነው፡፡››
“ኧረ..? እና ለዚህ ነው፣ ባልጠፋ ጊዜ በታህሳስ የዘራውን ሰብል እንዳይሰበስብ የሰማይ ወፎች አይዘሩም አያጭዱም የሰማይ አባታቸው ይመግባቸዋል እንጂ፤ ብሎ የሚስብክ ቤተክርስቲያን ማህበረሰብን
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
አባይ ማደሪያ የለው ግንድ ይዞይዞራል፡፡ ከልጅነቴ ጀምሮ አባይ፣ አባይ ሲባል እየሰማሁ ነው ያደኩት፡፡ በውስጤ አባይ ግዙፍ ነው፡፡ ወደ ድልድዩ እየተጠጋን ነው፡፡ አሁን በደንብ ወንዙ ይታየኛል፡፡ የአለም እረጅሙን ወንዝ አባይ...፣ በሱዳን አቋርጦ፣ ግብፅን አጠጥቶ፣ ተርፎ
ሜድትራያንያን ባህር የሚገባው አባይ... ፣ በሁሉም አቅጣጫ ለማየት ሞከርኩ፣ በደንብ ተንጠራራሁ፣ አባይ እንደጠበኩት ግዙፍ አልሆንልህ አለኝ፡፡ ውስጤ አግዝፌው ስለነበር ይሆን?፣ ወይስ ገና ከዚህ ወዲያ ነው ሚገዝፈው...? ይሄን እንዴት እስከዛሬ ሳንገድብ ቆየን? እነዚህ
ሃሳቦች በውስጤ ተሯሯጡ፡፡
ልጅቷ ነቃች፡፡ ዐይኗን እያሻሸች ቀና ብላ አየችኝ፡፡
“እንቅልፋም!” አልኳት፡፡
ፈገግ ብላ፣ “ብዙ ተኛሁ እንዴ?”
“እንጃ፣ እያነበብኩ ነበር፤ አላስተዋልኩም፡፡”
“መፅሀፉ አሪፍ ነው አይደል?”
“በጣም ምርጥ ነው፡፡ ይቅርታ ተሳስቻለሁ፡፡”
“ችግር የለውም፡፡ እንኳን ተመቸህ፡፡”
“እንደውም አልሰጥሽም፤ ወስጄዋለሁ፤” አልኩኝ ፈገግ ብዬ፡፡
“ችግር የለውም፡፡ ሌላ እገዛለሁ፡፡”
“ዋጋውን ግን፣ በእጥፍ እከፍላሁ::”
“በጭራሽ አይሆንም፡፡ እንደውም ስጦታዬ ነው፡፡”
“እንዴ ለምን?፣ምን አድርጌልሽ?››
«እንደ ፍራሽ ተኝቼብህ ለመጣሁት፡፡”
“ከተማሪማ ስጦታ አልቀበልም፤” አልኩኝ ሆን ብዬ፤ ገና አሁን እንተዋወቅ ላለማለት፡፡
“ማነው ተማሪ ናት ያለህ?”
“ውይ ለካ በደንብ ሳንተዋወቅ ነው፤ ወደ ወሬ የገባነው፡፡ ያቤዝ እባላለሁ።”
“ህይወት፡፡ ስምህ ደስ ሲል፡፡ ምን ማለት ነው?”
“እ...፣ በችግር ውስጥ የተወለደና ለችግሩ መፍትሄ የሆነ ማለት
ነው ሲሉ ሰምቻለው፡፡”
“ትርጉሙም ስሙም በጣም ደስ ይላል፡፡”
“ይሆናል፡፡ እኔ ግን እስካሁን ችግር እንጂ፣ የችግር መፍትሄ ሆኜ አላውቅም፡፡”
“ወደፊት ትሆናለሃ፡፡”
ሃሃሃ...ወደፊት ትሆናለህ'፣ ወደፊቴን ላጠፋው እየሄድኩ እንደሆነ ብታውቂ..፣ በውስጤ አልጎመጎምኩ፡፡ ዳግሞ መፅሀፉን ገለጥኩት፡፡ አላባበለኝም፡፡ በፍጥነት ጭልጥ አድርጎ አስመጠኝ፡፡ ላድናት ጥፍሬን ያሾልኩለት ቆንጅዬ፣ ዳግም አጠገቤ እንደሌለች እረሳኋት፡፡
መልሳ ጋደም አለችብኝ፡፡ አሁን ቤተኛ ሆነናል፡፡ ቀጥታ ታፋዎቼ ላይ ተጋደመች፡፡ ቀይ፣ ለጋና ሰልካካ ፊቷን አየሁት፡፡ ያስጎመዣል፡፡ የሹራብ ጃኬቴን አውልቄ እንድትንተራሰው ሰጠኋት፡፡ ተቀበለችኝ፡፡ መፅሀፉ ግን ማግኔት ነው፡፡ መልሶ ወደ ራሱ ይጎትተኛል፡፡ ወታደሩ የህዝቡን አመፅ እንዴት ወደራሱ ጠምዝዞ እንደቀለበሰው፣ አተራረኩ ይገርማል፡፡ ሻለቃ መንግስቱ በደርጉ ምስረታ ስብሰባ ላይ ባደረገው ዲስኩር፣ እንዴት የሰው
ልብ እንደገዛ ማንበብ ይመስጣል፡፡ የዚያው የመጀምሪያ ቀን ዲስኩር
ማሳረጊያ 'ኢትዮጵያ ትቅደም' መፈክር፣ የሀገሪቷ የአስራ ሰባት ዓመት ቋንቋ መሆኑን ማንበብ ይደንቃል፡፡ አብዛኛውም የሃገራችን ፖለቲካ መዘወሪያ ሃሳቦች እንደዚህ ባሉ ቅፅበታዊና ስሜታዊ ሁኔታ ሚፈጠሩ ይሆን እንዴ ብዬ አሰላሰልኩ፡፡
ህይወት ትገላበጣለች፡፡ ታፋዎቼ መሀል ሞቀኝ፡፡ አሁን ትኩረቴ ሲበተን ታወቀኝ፡፡ የሚሰማኝ ሙቀት፣ ካሰመጠኝ ድንቅ መፅሀፍ፣ እየጎተተ አውጥቶ፣ ትኩረቴን ወደ እርሷ እያደረገው ነው፡፡ ስለእርሷ
ማሰብ ጀመርኩ፡፡ እያነበብኩ፣ አንድ እጄን ጭንቅላቷ ላይ ጣልኩት፡፡
ፀጉሯን መደባበስ ጀመርኩ፡፡ በስሱ ፊቷን ዳበስኩት፡፡ ያፍንጫዋን ስልካካነት ወደታች በስሱ ወረድኩት፣ እናት ልጇን እንደምትዳብሰው፤ ፍቅረኛማቾች እንደሚደባበሱት፣ የከንፈሮቿን ጠርዝ እየተከተልኩ በጣቶቼ ጫፍ ዳበስኳቸው፡፡ ዝም፣ ጭጭ፡፡ መልሼ፣ በፀጉሮቿ መሀል
ጣቶቼን ላኳቸው፡፡ አሁን፣ መፅሀፉን ለይስሙላ ነው የያዝኩት፡፡ እያነበብኩት አይደለም፡፡
ስሜቴ እየሞቀ መጥቷል፡፡ እንቅልፍ ካልወሰዳት፣ የተኛችበት ታፋዎቼ መሀከል ያለው እንቅስቃሴ፣ አፍ አውጥቶ ይናገራል፡፡ አዎ እንቅልፍ ካልወሰዳት፣ እኔ ምንም መናገር አይጠበቅብኝም፡፡ መፅሀፉን ዘግቼ አስቀመጥኩት፡፡ ትኩር ብዬ፣ ቁልቁል እንደ ፍቅረኛ እያየኋት
ነው፡፡ የሌሎች ተሳፋሪዎችን ዐይንና ቀልብ ከሳብን ቆይተናል፡፡ አብረን
የመጣን ፍቅረኛሞች፣ ባልና ሚስት እንጂ፣ በድንገት እዚሁ የተገናኘን
አንመስልም፡፡ ተሳፋሪዎች በአግራሞት እየተመለከቱን ነው፡፡ ህይወት በጣም ቀላል፣ተግባቢና መስህብ ያላት ቆንጆ ነች፡፡ በጣም የምንዋደድ ፍቅረኛሞች እንመስላለን፡፡
ትወስደዋለህ፤ እስጥሃለሁ፤ ያለችኝ ውልብ አለብኝ፡፡ አሁን ለእኔ ጊዜ ስጠኝ መፅሀፉን ሌላ ጊዜ ታነበዋለህ ማለቷ ይሆን? ስሜቴ ሲያድግ ታወቀኝ፡፡ አሁን እንኳን ማንበብ፣ ዐይኔን እንኳ ከእርሷ መንቀል አልቻልኩም፡፡ እዳብሳታለሁ፡፡ እየሰማች ከሆነ፣ ታፋዎቼ መሀከል
የተፈጠረው እሳተ ጎሞራ፣ ስሜቴን በማያወላዳ መልኩ ያሳብቅልኛል፡፡
ማስረዳት አይጠበቅብኝም፡፡ እንቅልፍ እንዳልወስዳት ማረጋገጥ አለብኝ፡፡
ስሜቴን እየሰማችው መሆን አለመሆኑን ማወቅ አለብኝ፡፡ ትኩር ብዬ አየኋት፡፡ ቁልቁል የተንሰለከከ አፍንጫዋን በጣቶቼ በፍቅር እየዳሰስኩት ወረድኩኝ፡፡ ቁልቁል ወርጄ ጫፍ ላይ ስደርስ፣ በጣቶቼ ቀስ ብዬ አፍንጫዋን ጭምቅ፣ እፍን አደረኳት፡፡ ወዲያው ቀና ብላ፣
“ልትገለኝ ነው እንዴ?” አለችኝ፡፡
ፈገግ ብዬ፣ “እና ጥለሽኝ ስትተኚ...”
“አንተስ ጥለኸኝ በመፅሃፉ ስትመሰጥ አልነበር፡፡”
“የእውነት፡፡ መፅሀፉ ውበትሽን ሚገዳደር ነው፡፡”
“ፖለቲካ ትወዳለህ ማለት ነው፡፡”
“እንደዛ ሳይሆን፣ የያ ትውልድ ታሪክ ይማርከኛል፡፡
ችሎታቸው፣ ዲሲፕሊናቸው፣ የሀገር ፍቅራቸው፣ አሁን እንኳን ሀገር እየመሩም እየተቃወሙም ያሉት እነሱ እኮ ናቸው፡፡”
“አሁን ወጣቱ ሁሉ ፖለቲከኛ አይደል እንዴ?”
“ማለቴ፣ አሁን ያለችው ኢትዮጵያ የዛ ትውልድ የአዕምሮ ውጤትና የእጅ ስራ እየሆነችኮ ነው፡፡ ያ ትውልድ መሬት ላራሹ ብሎ ፊውዳሊዝምን በታተነ፡፡ ኢትዮጵያዊ ማነው ብሎ ሞግቶ፣ የብሄር ብሄረሰብን መልክ፣ መልኬ ነው ብላ እምትቀበል ኢትዮጵያን እጇን ጠምዝዞ እየገነባ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የብሄር ብሄረስብ ነች ብለው፣ መሀል አዲስ አበባ ላይ የብሄር ብሄረሰብ አደባባይ አኑረዋል፡፡ ወደድንም ጠላንም
አሻራ ያላቸው ትልቅ ትውልዶች ናቸው፡፡ እኛ በእነሱ ጥላ ተከልለን አሻራ ቢስ ሆነን ልናልፍ ነው፡፡”
“ግን ያ ትውልድ፣ ያልከው ብቻ አይደለም እኮ፡፡ አስተዋዩና ባለ ልዩ አምሮ ያልከው ያ ትውልድ፣ እርስ በርሱ ተባልቷል፡፡ ወንድም ወንድሙን ገሏል፧ ኢትዮጵያዊ ባህል ባልሆነ ጭካኔ ሀገሪቷ የደም
አኬልዳማ አድርጓታል፡፡ ዘጠና ዘጠኝ ከመቶ በላይ አማኝ በሆነ ማሀበረሰብ፣ ከማርክስ ሌኒኒስት አስተምሮ ተነስቶ፣ ሀይማኖት የቀኝ ገዢዎች የማህበረሰብ ማደንዘዣ ድሪቶ ነው፤ አውልቁና ጣሉት አለ፡፡ ማህበረሰቡን እሴት አልባ አደረገው፡፡ መሰረቅ ባህላችን ሆነ፡፡አረ ስንቱን ..::”
“የእርስ በእርስ ጦርነቱን እንኳን ተይው፣ እንደ አንድ የማህበረሰቡ ባህልና እሴት አብሮን የኖረ ነው፡፡ ግን ቆይ ቆይ፣ ሀይማኖት ማህበረሰባችን አላደነዘዘም እያልሽኝ ነው? የሆነ ችግር ሲያጋጥመው
ለመፍታት ከመጣር ይልቅ፣ ሁሉ ለበጎ ነው ብሎ ችግሩን ተላምዶ እንዲኖር ሀይማኖት አላደረገውም እያልሽኝ ነው?”
‹‹ሀይማኖታችን የሚለው ያልሰራ እርሱ አይብላ ነው፡፡››
“ኧረ..? እና ለዚህ ነው፣ ባልጠፋ ጊዜ በታህሳስ የዘራውን ሰብል እንዳይሰበስብ የሰማይ ወፎች አይዘሩም አያጭዱም የሰማይ አባታቸው ይመግባቸዋል እንጂ፤ ብሎ የሚስብክ ቤተክርስቲያን ማህበረሰብን
👍4❤1
አላደነዘዘም፣ አላሳነፈም እያልሽኝ ነው?”
“ቤተክርስቲያን ለኢትዮጵያ ባለ ውለታ ነች፡፡ ፊደልን ቀርፃ እውቀት ያስፋፋች ሀገራችንን ከቀኝ ግዛት እንድንከላከል ያነቃች።የሀገራችንን የደን ሀብት ተጠብቆ እንዲቆይ የረዳች፡፡ ሀገር በቀል እውቀት እንዲስፋፋ ጥንስስ የሆነች፡፡ ኢትዮጵያዊ ዜማን የፈጠረች፡፡ዓለም ዜማን በፅሁፍ ማስፈር ሳያውቅ እነ ቅዱስ ያሬድ የዛሬ አንድ ሺህ አምስት መቶ ዓመት ዜማን ደርሰው በፅሁፍ እንዲያሰፍሩ ኮትኩታ
ያሳደገች ቤተክርስቲያን ነች፡፡ተዉ እንጂ አወቅን ብላችሁ ቤተክርስቲያንን ውለታ ቢስ አታድርጓት፤” አለችኝ፡፡ ሥሜታዊ እየሆነች ነው፡፡
“ወዴት ወዴት..? ቤተክርስቲያን ውለታ የላትም አላልኩም፡፡ አንቺ ያልሻቸው በሙሉ እውነት ናቸው፡፡መቶ በመቶ
እስማማባቸዋለሁ፡፡ ሁሉም ነገር ጥሩ ጎን እንዳለው ሁሉ፣ መጥፎም ሊኖረው ይችላል፡፡ ቤተክርስቲያንም እንደዛው፡፡ ጥያቄው ሁሉንም በእውቀት መመርመር አለብን ነው፡፡ አይነኬ የምንላቸው ነገሮች፣
ለመመርመር የምንፈራቸው ነገሮች፣ የዘመናት ችግራችን ምክንያት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡”
“ቆይ ፊደል ቆጥራ ባስተማረች፣ ቤተክርስቲያንን ተማርን ብላችሁ መልሳችሁ እርሷ ላይ የምትዘምቱት ምን ይሁን ብላችሁ ነው?
በቃ አወቅን ካላችሁ የሚጠቅም ስራ ስሩ፡፡ እጃችሁን ከቤተከርስቲያን
አንሱ!” ተንገሸገሸች፡፡
“እንዲህ የምትናደጂ ከሆነ ወሬ እንቀይር፡፡”
“ኧረ እኔ አልተናደድኩም፡፡ ምን ያናድደኛል?”
“እንዴ! ከዚህ በላይ ምን ትሆኚ? ተንጨረጨርሽ እኮ፡፡”
“ተናድጄ ሳይሆን፣ ሁሉም አወኩ ባይ ተነስቶ እጁን ቤተክርስቲያን ላይ ሲያነሳ ያበሳጨኛል፡፡”
“ሲጀመር፣ እኔ ተማርኩ ባይ አይደለሁም ሀይማኖት ሴንሲቲቭ ኢሹ' እንደሆነ ይገባኛል፡፡ ግን እንደማህበረሰብ የባህል
አብዮት ያስፈልጋል ብዬ አምናለሁ፡፡ ለምሳሌ፤ የመስራት ባህላችን፣የሚስራን ከማበረታታት ይልቅ መንቀፍ፣ ተነጋግሮ የመግባባት ልምዳችን፣ በአጠቃላይ ማህበራዊ ባህሎቻችን መፈተሽ አለባቸው ባይ ነኝ፡፡ እኛ ሀገር ደግሞ፣ የባህላችን መነሻም፣ መንገዱም፣ መድረሻምውም ሀይማኖት ነው። እሱን ካልፈተሸን የትም አንደርስም፡፡”
“እስቲ ቆይ፣ ቤተክርስቲያ ምን እንዳደረገቻችሁ አንድ ሁለት ብለህ አስረዳኝ፡፡” ፊቷ ላይ የንዴት ነበልባል ተንቀለቀለ፡፡ አባይ በረሃን ወጥተን የደጀን ከተማን እየተጨቃጨቅን ሳናያት አለፍን፡፡
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
“ቤተክርስቲያን ለኢትዮጵያ ባለ ውለታ ነች፡፡ ፊደልን ቀርፃ እውቀት ያስፋፋች ሀገራችንን ከቀኝ ግዛት እንድንከላከል ያነቃች።የሀገራችንን የደን ሀብት ተጠብቆ እንዲቆይ የረዳች፡፡ ሀገር በቀል እውቀት እንዲስፋፋ ጥንስስ የሆነች፡፡ ኢትዮጵያዊ ዜማን የፈጠረች፡፡ዓለም ዜማን በፅሁፍ ማስፈር ሳያውቅ እነ ቅዱስ ያሬድ የዛሬ አንድ ሺህ አምስት መቶ ዓመት ዜማን ደርሰው በፅሁፍ እንዲያሰፍሩ ኮትኩታ
ያሳደገች ቤተክርስቲያን ነች፡፡ተዉ እንጂ አወቅን ብላችሁ ቤተክርስቲያንን ውለታ ቢስ አታድርጓት፤” አለችኝ፡፡ ሥሜታዊ እየሆነች ነው፡፡
“ወዴት ወዴት..? ቤተክርስቲያን ውለታ የላትም አላልኩም፡፡ አንቺ ያልሻቸው በሙሉ እውነት ናቸው፡፡መቶ በመቶ
እስማማባቸዋለሁ፡፡ ሁሉም ነገር ጥሩ ጎን እንዳለው ሁሉ፣ መጥፎም ሊኖረው ይችላል፡፡ ቤተክርስቲያንም እንደዛው፡፡ ጥያቄው ሁሉንም በእውቀት መመርመር አለብን ነው፡፡ አይነኬ የምንላቸው ነገሮች፣
ለመመርመር የምንፈራቸው ነገሮች፣ የዘመናት ችግራችን ምክንያት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡”
“ቆይ ፊደል ቆጥራ ባስተማረች፣ ቤተክርስቲያንን ተማርን ብላችሁ መልሳችሁ እርሷ ላይ የምትዘምቱት ምን ይሁን ብላችሁ ነው?
በቃ አወቅን ካላችሁ የሚጠቅም ስራ ስሩ፡፡ እጃችሁን ከቤተከርስቲያን
አንሱ!” ተንገሸገሸች፡፡
“እንዲህ የምትናደጂ ከሆነ ወሬ እንቀይር፡፡”
“ኧረ እኔ አልተናደድኩም፡፡ ምን ያናድደኛል?”
“እንዴ! ከዚህ በላይ ምን ትሆኚ? ተንጨረጨርሽ እኮ፡፡”
“ተናድጄ ሳይሆን፣ ሁሉም አወኩ ባይ ተነስቶ እጁን ቤተክርስቲያን ላይ ሲያነሳ ያበሳጨኛል፡፡”
“ሲጀመር፣ እኔ ተማርኩ ባይ አይደለሁም ሀይማኖት ሴንሲቲቭ ኢሹ' እንደሆነ ይገባኛል፡፡ ግን እንደማህበረሰብ የባህል
አብዮት ያስፈልጋል ብዬ አምናለሁ፡፡ ለምሳሌ፤ የመስራት ባህላችን፣የሚስራን ከማበረታታት ይልቅ መንቀፍ፣ ተነጋግሮ የመግባባት ልምዳችን፣ በአጠቃላይ ማህበራዊ ባህሎቻችን መፈተሽ አለባቸው ባይ ነኝ፡፡ እኛ ሀገር ደግሞ፣ የባህላችን መነሻም፣ መንገዱም፣ መድረሻምውም ሀይማኖት ነው። እሱን ካልፈተሸን የትም አንደርስም፡፡”
“እስቲ ቆይ፣ ቤተክርስቲያ ምን እንዳደረገቻችሁ አንድ ሁለት ብለህ አስረዳኝ፡፡” ፊቷ ላይ የንዴት ነበልባል ተንቀለቀለ፡፡ አባይ በረሃን ወጥተን የደጀን ከተማን እየተጨቃጨቅን ሳናያት አለፍን፡፡
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
...“ይቺ በመቀጨጭ ላይ ያለችዋ ” አሉ ዮናታን' ወደ ቆርቆሮው ውስጥ በጣታቸው እያመለከቱ።
“ እም ፡ አዎ ከእንግዲህ የምታድግ አትመስልም ”አሉ ዶክተር አጥናፉ ፥ ብዙም ባልተደነቀ ስሜት ።
“ ከምን የመጣ ይመስልሃል ? ” አሉ ዮናታን ፡ ዐይናቸውን ወደ እስጉብኝው እያሸጋገሩ ።
“ አካባቢው ኣልተስማማት ይሆናላ ! ” አሉ ዶክተር አጥናፉ ፡ በቀልድ ዐይነት ! “ ወይም ደግሞ ፍሬዋ ከጓደኞቿ ተለይታ በተለየ ዐፈር ውስጥ መብቀል ፈልጋ ይሆናል ። ”
ከት ብሎም ባይስቅ እስጐብኝው ፈገግ አለ ። ዮናታን ግን የተቋጠረው ግንባራቸው አልተፈታም " ይብሱን ነገሩን
አጠንክረው
“ የአካባቢም ተጽፏኖ ሆና የዐፈሩ አለመማማት ፥ወይም ሌላ ችግር ፡ የስንዴዋ መቀጨጭ ከአያያዝ ግድየለሽ
ነት የመጣ ነው ። ገና ከእንጭጭነት ችግሯን አስተውሉ አካባቢዋን ወይም አፈሯን መለወጥ ቢቻል ኖሮ ለዚህ አት
ደርስም ነበር ። ግን አንድ ነች ። አንድ ነገር አንድ ነውና አብዛኛውን ጊዜ አናስብበትም ። አናስተውሰውም ። ጣሳው ሙሉ ተክል ሊበላሽ ቢሆን ኖሮ ግን ወዲያው መፍትሔ በተ ፈለገለት ነበር
አስጐብኝው በድንጋጤ ክው ብሎ ቀረ አምርረዋል ወይሰ ይቀልዳሉ ? ” አለ በልቡ እሱም ። አማካሪው ዶክተር ኤጥናፉ ቸል ያሉትን ነገር ዮናታን አምርረው መያዛቸው ምክንያቱ አልገባህ አለው ። “ ምነው ባልጋበዝኳችው ! ” አለ በልቡ ፡ አነጋገራቸው ዶክተር አጥናፉን
ይላውጥብኛል ብሎ ስለፈራ ዮናታንን በጥላቻ እያያቸው
“ ይህ እኮ አብዛኛውን ጊዜ ሊደርስ የሚችል አጋጣሚ ነው ። ደግሞስ የአንዱ መቀጨጭ ምን ያህል ይጎዳል ብለህ
ነው ? የዐፈሩ ተጽዕኖ በአብዛኛው ስንዴ ዕድገት ሲለካ ይችላል ዶክተር ፡ አሁንም ለነጎሩ ክብዶት ሳይሰጠት ።
“ ይጐዳል እንጂ እንዴት አይጐዳም ?” አሉ ዮናታን አምርረው ። “ የቆርቆሮው ተክል እኮ ስምንት የምታሰኘው
ይህቺ አንዷ ስትጨርስ ነበር ስትጐድል ግን ሰባት ታረገዋለች።አንድ ሳንቲም “ ዋጋ የለውም” እንላለን ። ግን “ ዋጋ
እንዳልው የምንረዳው አራት ሳንቲም ይዘን ስንቀር ነው ”
አስጐብኝው የባሰውን በጥላቻ ገላመጣቸው ። እሳቸው ግን ልብ አላሉትም ። እሱን መጉዳታቸውም አልታወቃችውም ። ዶክተር አጥናፉ ራሳቸው፣ “ሰውዬው አበደ እንዴ?”
በማለት ዐይነት በሆዳቸው እየሣቁ ፥ ምንም ሊጠይቁ ወይም ሊናገሩ ስላልቻሉ ዝም አሉ ።
ከጥቂት ዝምታ በኋላ ዮናታን ልምጭጭ ፈገግታ እያሳዩ' በምጸታዊ አነጋገር “ አየህ የአቤልም ነገር እንዲሁ ነው ” አሏቸው ።
ዶክተር አጥናፉ የዮናታን ውስጣዊ ስሜት እንዲህ የተለዋወጠበት ምክንያት ያው ገባቸው ። ስለ አቤል ጉዳይ ደጋግመው አነጋግረዋቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ለጉዳዩ ብዙም ክብደት ወይም አትኩሮት ባለመስጠት ቸል ብለውት ስለቆዩ
አሁን ጥያቄም ይሁን መልስ ማንሣት አልፈለጉም። ሐሳባቸውን ሁሉ ወደ ተክሉ በመሰብሰብ ዐይነት ከአስጐብኝው
ጋር ሐሳብ በመለዋወጥ ዮናታን የተነሡበትን ሐሳብ ለማዘናጋት ሞከሩ ። ይሁን እንጂ ፥ ዮናታን ውስጥ የሚንቦገቦገው ሐሳብ በቀላሉ የሚበርድ አልነበረም። ጉብኝቱን ጨርሰው
ከተክሉ ቤት ሲወጡ እንደ ገና አነሡባቸው ።
“ ሁላችሁም የዚህን ልጅ ጉዳይ ቸል ማለታችሁ ነው ? ያቤልን?እንዴትነው? አሁንም አልተሻለው?” አሉ ዶክተር
አጥናፉ ሸሽተው የማያመልጡት ነገር መሆኑን ገምተው ።
ይሻለዋል ? ጉንፋን ” ኮ አይደለም ያመመው ።ይህኛው አነጋገራቸው ቁጣ ብቻ ሳይሆን ተስፋ መቁረጥም
ነበረበት ።
የዮናታን አነጋገር ዶክተር አጥናፉን አላስቆጣቸውም ።የቅርብ ጓደኝነት ስላላቸው አንዳቸው የአንዳቸውን ጸባይ ጠንቅቀው ያውቃሉ፡ዮናታን ከውስጥ ሥቀው ከላይ ጥርሳቸውን ማሳየት አይችሉም ። የተማረሩበትን ወይም የበሽቁበትን ነገር ማንም ፊት ይሁን ከማንም ጋር ፊትለፊት በቁጣ ተናግረው ነው የሚወጡት ። ከዚያ ንዴቱ ቢበርድላቸው ያው ሰው አክባሪነታችው ፍቅር የተሞላበት ሰላምታችሙ
ዮናታንነታቸው ይመለሳል ። ነገር ግን የዚህ ልጅጉዳይ ይህን ያህል ለምን እንዳንገበገባቸው ዶክተር አጥናፉ ጥርት ብሎ ሊታያቸው አልቻለም ።
“ ችግሩ ኮ! ” አሉ ዶክተር አጥናፉ፥ የዮናታንን ቁጣ ማስታገሥ በሚችል ለዘብ ያለ አነጋገር ። “ ችግሩ የሁሉም አለመተባበር ነው ። ከአሁን በፊት በዩኒቨርስቲው ውስጥ እንዲህ ዐይነት ጉዳይ ትልቅ አትኩሮት ተሰጥቶት
ስላልተሠራ አሁንም ...
ዮናታን አላስጨረሳቸውም ።
“ እኔም እኮ የምለው ይህንኑ ነው ። ለምን አትኩሮት አይሰጠውም ? በማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ካሉት ችግሮች አንዱ
አይደለም ወይ? አየህ ! ፍቅር ሲሠምር ፥ ሲገኝ ሲያብብ ደስታ ፍሥሐ ነው ። ከመገኘቱ በፊት ወይም ተግኝቶ ሲጠፋ ኃይለኛ ጥማት ፡ ሥቃይ ሕመም ነው ፥ ” አሉና፡ ነገሩን ከውሉጋር እንደማያያዝ ትንሽ ካሰቡ በኋላ ፥ “ አዎ ! እና ፥ ምንም
ይሁን ምን የ ግለሰብን ከዓላማው ወይም ከግቡ የሚያዘናጋ ወይም ራሱን የሚያስጠላ ሁኔታ እስከሆነ ድረስ መድኃኒቱ መፈለግ አለበት አሁን አቤል በዚህ ሁኔታ ተጨናግፎ ትምህርቱን ቢያቋርጥ ወይም ተደባብሶ ቢመረቅ ፡ ሁለተኛ ወደ ትምህርትና ምርምር ዓለም ፊቱን እንደማይመልስ አታውቅም ? ”
“ እሱ እንኳን በጤናቸው የሚመረቁትም የአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ጸባይ ነው ። ሺ አስመርቀናል ፤ ነገር ግን
ምንም ተአምር የሠራ አላየንም አሉ ዶክተር አጥናፉ በንቀትና ተስፋ በቆረጠ ስሜት ።
ይህ የሚሆነው ለምን ይመስልሃል ? ! በእኔ ግምት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቶቻቸውን በፍቅር እንዲጀምሩ
ስለማናደርጋቸው ነው ።ሳያስቡት ዶክተር አጥናፉ ቢሮ ስለ ደረሱ ። በሩን ለመ
ክፈት ቁልፉን እየጠመዘዙ አሁንም በተሰላቸና ነገሩን ቶሎ ለመቁረጥ በዳዳ ስሜት • “ ብቻ ሁሉም ነገሩን እንዳንተ
ቢያስብበት ምናልባት ውጤት ያገኝ ይሆናል ። ግን እንዳየሁት ይህን ጉዳይ ብሎ ኮሚቴ ላይ አቅርቦ መፍትሔ ለመ
ፈለግ የሚሻ ሰው እንጂ ”
“ ይህ ከምን የመጣ ይመስልሃል ? ” አሉ ዮናታን ፥ ተከትለዋቸው ወደ ቢሮ ውስጥ እየገቡ ፤ ይህ ራሱ ምሁርነታችን የሚያስከትልብን በሽታ ራሳችንን በጣም ከፍ አድርገን ስለምንግምት ከኛ በኋላ ሰው የሚፈጠር አይመስለንም ። ዐይናችንን ገልጠን ከተማሪዎቻችን መሐል ታላላቅ ሰዎች ሊበቅሉ እንደሚችሉ ማየትና መገመት አለብን ።
ይህ ስሜት ሲኖረን ብቻ ነው ተማሪዎቻችን እንቅፋት እንዳይመታቸው ልንጠነቀቅላቸው የምንችለው ”
“ ስደበና! ” አሉና ዶክተር አጥናፉ በቀልድ ፡ “ ለማንኛውም እስኪ ቁጭ በል” ሲሉ ዮናታንን ጋበዟቸው ።
“ አልቀመጥም ” አሉ ዮናታን ሰዓታቸውን እየተመለከቱ። “ ኦ! እንዲያውም ሰዓት አሳለፍን ። በአሥር ሰዓት አንድ ተማሪ ቀጥሬ ነበር።
“ እሺ እስቲ እንግዲህ በሚቻለን መንገድ እንታግሳለና ! ” አሉ ዶክተር አጥናፉ " ጉዳዩ ከውስጥ ባይፈነቅላቸውም ዮናታንን ለማስደስት ያህል "
“ በውነት እንዲያው በሚቻለን መንገድ ይህንን ልጅ መርዳት አለብን ። እባክህ ቸል አትበል ” አሉ ዮናታንም ረጋ ባለ አንደበትና ረዳት በሚፈልግ ስሜት ወደ
ከዚያ ፥
ወዲያው ወጥተው በመኪናቸው ወደ ስድስት ኪሎ በረሩ ። ከቢሮአቸው ሲደርሱ እስክንድር መዝጊያን
ተደግፎ ቆሞ አገኙት።
““ ሶሪ ዘግየሁብህ አይደለም ? ” አሉት በሩን ለመክፈት እየተቻኮሉ ። ዐሥር ደቂቃ አሳልፈውበት ነበር ።ጠዋት ገለጻ ክፍላቸው ውስጥ ክፍለ ጊዜኣቸውን ጨርሰው ሲወጡ ነበር በዚህ ሰዓት እንዲያገኛቸው የቀጠሩት ። የፈለጉት ለአቤል ጉዳይ መሆኑን ፈጽሞ አልተጠራ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
...“ይቺ በመቀጨጭ ላይ ያለችዋ ” አሉ ዮናታን' ወደ ቆርቆሮው ውስጥ በጣታቸው እያመለከቱ።
“ እም ፡ አዎ ከእንግዲህ የምታድግ አትመስልም ”አሉ ዶክተር አጥናፉ ፥ ብዙም ባልተደነቀ ስሜት ።
“ ከምን የመጣ ይመስልሃል ? ” አሉ ዮናታን ፡ ዐይናቸውን ወደ እስጉብኝው እያሸጋገሩ ።
“ አካባቢው ኣልተስማማት ይሆናላ ! ” አሉ ዶክተር አጥናፉ ፡ በቀልድ ዐይነት ! “ ወይም ደግሞ ፍሬዋ ከጓደኞቿ ተለይታ በተለየ ዐፈር ውስጥ መብቀል ፈልጋ ይሆናል ። ”
ከት ብሎም ባይስቅ እስጐብኝው ፈገግ አለ ። ዮናታን ግን የተቋጠረው ግንባራቸው አልተፈታም " ይብሱን ነገሩን
አጠንክረው
“ የአካባቢም ተጽፏኖ ሆና የዐፈሩ አለመማማት ፥ወይም ሌላ ችግር ፡ የስንዴዋ መቀጨጭ ከአያያዝ ግድየለሽ
ነት የመጣ ነው ። ገና ከእንጭጭነት ችግሯን አስተውሉ አካባቢዋን ወይም አፈሯን መለወጥ ቢቻል ኖሮ ለዚህ አት
ደርስም ነበር ። ግን አንድ ነች ። አንድ ነገር አንድ ነውና አብዛኛውን ጊዜ አናስብበትም ። አናስተውሰውም ። ጣሳው ሙሉ ተክል ሊበላሽ ቢሆን ኖሮ ግን ወዲያው መፍትሔ በተ ፈለገለት ነበር
አስጐብኝው በድንጋጤ ክው ብሎ ቀረ አምርረዋል ወይሰ ይቀልዳሉ ? ” አለ በልቡ እሱም ። አማካሪው ዶክተር ኤጥናፉ ቸል ያሉትን ነገር ዮናታን አምርረው መያዛቸው ምክንያቱ አልገባህ አለው ። “ ምነው ባልጋበዝኳችው ! ” አለ በልቡ ፡ አነጋገራቸው ዶክተር አጥናፉን
ይላውጥብኛል ብሎ ስለፈራ ዮናታንን በጥላቻ እያያቸው
“ ይህ እኮ አብዛኛውን ጊዜ ሊደርስ የሚችል አጋጣሚ ነው ። ደግሞስ የአንዱ መቀጨጭ ምን ያህል ይጎዳል ብለህ
ነው ? የዐፈሩ ተጽዕኖ በአብዛኛው ስንዴ ዕድገት ሲለካ ይችላል ዶክተር ፡ አሁንም ለነጎሩ ክብዶት ሳይሰጠት ።
“ ይጐዳል እንጂ እንዴት አይጐዳም ?” አሉ ዮናታን አምርረው ። “ የቆርቆሮው ተክል እኮ ስምንት የምታሰኘው
ይህቺ አንዷ ስትጨርስ ነበር ስትጐድል ግን ሰባት ታረገዋለች።አንድ ሳንቲም “ ዋጋ የለውም” እንላለን ። ግን “ ዋጋ
እንዳልው የምንረዳው አራት ሳንቲም ይዘን ስንቀር ነው ”
አስጐብኝው የባሰውን በጥላቻ ገላመጣቸው ። እሳቸው ግን ልብ አላሉትም ። እሱን መጉዳታቸውም አልታወቃችውም ። ዶክተር አጥናፉ ራሳቸው፣ “ሰውዬው አበደ እንዴ?”
በማለት ዐይነት በሆዳቸው እየሣቁ ፥ ምንም ሊጠይቁ ወይም ሊናገሩ ስላልቻሉ ዝም አሉ ።
ከጥቂት ዝምታ በኋላ ዮናታን ልምጭጭ ፈገግታ እያሳዩ' በምጸታዊ አነጋገር “ አየህ የአቤልም ነገር እንዲሁ ነው ” አሏቸው ።
ዶክተር አጥናፉ የዮናታን ውስጣዊ ስሜት እንዲህ የተለዋወጠበት ምክንያት ያው ገባቸው ። ስለ አቤል ጉዳይ ደጋግመው አነጋግረዋቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ለጉዳዩ ብዙም ክብደት ወይም አትኩሮት ባለመስጠት ቸል ብለውት ስለቆዩ
አሁን ጥያቄም ይሁን መልስ ማንሣት አልፈለጉም። ሐሳባቸውን ሁሉ ወደ ተክሉ በመሰብሰብ ዐይነት ከአስጐብኝው
ጋር ሐሳብ በመለዋወጥ ዮናታን የተነሡበትን ሐሳብ ለማዘናጋት ሞከሩ ። ይሁን እንጂ ፥ ዮናታን ውስጥ የሚንቦገቦገው ሐሳብ በቀላሉ የሚበርድ አልነበረም። ጉብኝቱን ጨርሰው
ከተክሉ ቤት ሲወጡ እንደ ገና አነሡባቸው ።
“ ሁላችሁም የዚህን ልጅ ጉዳይ ቸል ማለታችሁ ነው ? ያቤልን?እንዴትነው? አሁንም አልተሻለው?” አሉ ዶክተር
አጥናፉ ሸሽተው የማያመልጡት ነገር መሆኑን ገምተው ።
ይሻለዋል ? ጉንፋን ” ኮ አይደለም ያመመው ።ይህኛው አነጋገራቸው ቁጣ ብቻ ሳይሆን ተስፋ መቁረጥም
ነበረበት ።
የዮናታን አነጋገር ዶክተር አጥናፉን አላስቆጣቸውም ።የቅርብ ጓደኝነት ስላላቸው አንዳቸው የአንዳቸውን ጸባይ ጠንቅቀው ያውቃሉ፡ዮናታን ከውስጥ ሥቀው ከላይ ጥርሳቸውን ማሳየት አይችሉም ። የተማረሩበትን ወይም የበሽቁበትን ነገር ማንም ፊት ይሁን ከማንም ጋር ፊትለፊት በቁጣ ተናግረው ነው የሚወጡት ። ከዚያ ንዴቱ ቢበርድላቸው ያው ሰው አክባሪነታችው ፍቅር የተሞላበት ሰላምታችሙ
ዮናታንነታቸው ይመለሳል ። ነገር ግን የዚህ ልጅጉዳይ ይህን ያህል ለምን እንዳንገበገባቸው ዶክተር አጥናፉ ጥርት ብሎ ሊታያቸው አልቻለም ።
“ ችግሩ ኮ! ” አሉ ዶክተር አጥናፉ፥ የዮናታንን ቁጣ ማስታገሥ በሚችል ለዘብ ያለ አነጋገር ። “ ችግሩ የሁሉም አለመተባበር ነው ። ከአሁን በፊት በዩኒቨርስቲው ውስጥ እንዲህ ዐይነት ጉዳይ ትልቅ አትኩሮት ተሰጥቶት
ስላልተሠራ አሁንም ...
ዮናታን አላስጨረሳቸውም ።
“ እኔም እኮ የምለው ይህንኑ ነው ። ለምን አትኩሮት አይሰጠውም ? በማኅበራዊ ኑሮ ውስጥ ካሉት ችግሮች አንዱ
አይደለም ወይ? አየህ ! ፍቅር ሲሠምር ፥ ሲገኝ ሲያብብ ደስታ ፍሥሐ ነው ። ከመገኘቱ በፊት ወይም ተግኝቶ ሲጠፋ ኃይለኛ ጥማት ፡ ሥቃይ ሕመም ነው ፥ ” አሉና፡ ነገሩን ከውሉጋር እንደማያያዝ ትንሽ ካሰቡ በኋላ ፥ “ አዎ ! እና ፥ ምንም
ይሁን ምን የ ግለሰብን ከዓላማው ወይም ከግቡ የሚያዘናጋ ወይም ራሱን የሚያስጠላ ሁኔታ እስከሆነ ድረስ መድኃኒቱ መፈለግ አለበት አሁን አቤል በዚህ ሁኔታ ተጨናግፎ ትምህርቱን ቢያቋርጥ ወይም ተደባብሶ ቢመረቅ ፡ ሁለተኛ ወደ ትምህርትና ምርምር ዓለም ፊቱን እንደማይመልስ አታውቅም ? ”
“ እሱ እንኳን በጤናቸው የሚመረቁትም የአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ጸባይ ነው ። ሺ አስመርቀናል ፤ ነገር ግን
ምንም ተአምር የሠራ አላየንም አሉ ዶክተር አጥናፉ በንቀትና ተስፋ በቆረጠ ስሜት ።
ይህ የሚሆነው ለምን ይመስልሃል ? ! በእኔ ግምት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቶቻቸውን በፍቅር እንዲጀምሩ
ስለማናደርጋቸው ነው ።ሳያስቡት ዶክተር አጥናፉ ቢሮ ስለ ደረሱ ። በሩን ለመ
ክፈት ቁልፉን እየጠመዘዙ አሁንም በተሰላቸና ነገሩን ቶሎ ለመቁረጥ በዳዳ ስሜት • “ ብቻ ሁሉም ነገሩን እንዳንተ
ቢያስብበት ምናልባት ውጤት ያገኝ ይሆናል ። ግን እንዳየሁት ይህን ጉዳይ ብሎ ኮሚቴ ላይ አቅርቦ መፍትሔ ለመ
ፈለግ የሚሻ ሰው እንጂ ”
“ ይህ ከምን የመጣ ይመስልሃል ? ” አሉ ዮናታን ፥ ተከትለዋቸው ወደ ቢሮ ውስጥ እየገቡ ፤ ይህ ራሱ ምሁርነታችን የሚያስከትልብን በሽታ ራሳችንን በጣም ከፍ አድርገን ስለምንግምት ከኛ በኋላ ሰው የሚፈጠር አይመስለንም ። ዐይናችንን ገልጠን ከተማሪዎቻችን መሐል ታላላቅ ሰዎች ሊበቅሉ እንደሚችሉ ማየትና መገመት አለብን ።
ይህ ስሜት ሲኖረን ብቻ ነው ተማሪዎቻችን እንቅፋት እንዳይመታቸው ልንጠነቀቅላቸው የምንችለው ”
“ ስደበና! ” አሉና ዶክተር አጥናፉ በቀልድ ፡ “ ለማንኛውም እስኪ ቁጭ በል” ሲሉ ዮናታንን ጋበዟቸው ።
“ አልቀመጥም ” አሉ ዮናታን ሰዓታቸውን እየተመለከቱ። “ ኦ! እንዲያውም ሰዓት አሳለፍን ። በአሥር ሰዓት አንድ ተማሪ ቀጥሬ ነበር።
“ እሺ እስቲ እንግዲህ በሚቻለን መንገድ እንታግሳለና ! ” አሉ ዶክተር አጥናፉ " ጉዳዩ ከውስጥ ባይፈነቅላቸውም ዮናታንን ለማስደስት ያህል "
“ በውነት እንዲያው በሚቻለን መንገድ ይህንን ልጅ መርዳት አለብን ። እባክህ ቸል አትበል ” አሉ ዮናታንም ረጋ ባለ አንደበትና ረዳት በሚፈልግ ስሜት ወደ
ከዚያ ፥
ወዲያው ወጥተው በመኪናቸው ወደ ስድስት ኪሎ በረሩ ። ከቢሮአቸው ሲደርሱ እስክንድር መዝጊያን
ተደግፎ ቆሞ አገኙት።
““ ሶሪ ዘግየሁብህ አይደለም ? ” አሉት በሩን ለመክፈት እየተቻኮሉ ። ዐሥር ደቂቃ አሳልፈውበት ነበር ።ጠዋት ገለጻ ክፍላቸው ውስጥ ክፍለ ጊዜኣቸውን ጨርሰው ሲወጡ ነበር በዚህ ሰዓት እንዲያገኛቸው የቀጠሩት ። የፈለጉት ለአቤል ጉዳይ መሆኑን ፈጽሞ አልተጠራ
ጠረም ምክንያቱም አቤል ከእሳቸው ገለጻ ክፍለ ጊዜ ሦስቱን ቀን
በተከታታይ አልገባም ። ክፍል ውስጥ ቢጠይቁት እስክንድር የሰጣቸው መልስ " ራሱን ትንሽ ስላመመው ነው ”ብሎ ነበር : ነግር ግን ደጋግሞ መቅረቱ ከዚህ የከፋ ሁኔታ ቢያጋጥመው ነው ብለው ስላሰቡ ስለሱ ሊጠይቁት ነው የቀጠሩት።
“ ስለ አቤል ልጠይቅህ ነበር'ኮ” አሉት ዮናታን ገና ቁጭ ከማለታቸው ፡ “ በእርግጥ በጠናው ነው ? ”
እስክንድር የተጠየቀው ያው የጠበቀውን ነገር ቢሆንም ስለ አቤል መስማትም ሆነ መናገር የማይፈልግበት ወቅት ነበር ። ሁኔታው ያበሽቀዋል ። ምንም ግልጽ የሆነለት ነግር የለም ። እንደጓኝነቱ ቀርቦ ቢያዋየው ፡ አባትነት በተሞላው ሁኔታ ቢያስታምመውም ፥ ቢያሻሽውም ፡ ቢኮረኩረውም ከአቤል ጠብ ያለ ነገር የለም ። አቤል አይናገርም ።አቤል ታፍኖ መሞት የሚፈልግ ሰው ነው ።
ስለ እሱ ሊጠይቁኝ እንደሆነ ጎብቶኛል ” አለ እስክንድር በቀደም እለት ምግብ አዳራሽ ሲገባ የሆነ ነገር አደናቅፎት ወድቆ ነበር ። ያን ያህል ጉዳት እንኳ አላገኘውም ፤ግን እንጃ ! ክፍልም አልገባም አለ ተኝቶ ነው የሚውለው
የመንፈስ መረበሽ መሰለኝ ።
“ እህ ! እንዲያ ነው ? ” አሉ ዮናታን ነገሩ ልባቸውን ቢከብደውም ኀዝናቸውን ለመደበቅ ሞክረው ምን መንፈሱ የተጐዳ ሰው'ኮ ዕንቅፋትም ይበቃዋል ። ”
“ እንደዚያ ሆኖ ነው መሰለኝ ”
ዮናታን ለደቂቃ ያህል ዝም አሉ : ብዙ ነገር ሐሳባቸው ውስጥ ብዙ ነገር እየተተራመሰባቸው ነበር እስክንድር የዮናታን ስሜት ምን ያህል ጭንቀት እንዶ ተወጣጠረ ከገጽታቸው ላይ ማንበብ ችሏል ። “ ይህን ያህል ለአንድ ተማሪ መጨነቃችን ምንድነው ? ” ሲል አሰበ ። ነገር ግን የአቤል ሁኔታ እሱን ራሱን እንዳስጨነቀው ባሰበ ጊዜ ዮናታንም ተመሳሳይ ስሜት ሊያድርባቸው እንደሚችል ገመተ ። ሐቀኛ ምሁር ነኝ
የሚተካውን ጠንካራ ተማሪ በጥቃቅን ማኅበራዊ ችግር ተደናቅፎ ሲቀር ማየት አይፈልግም ።
የዮናታን ሁኔታ ፡ በእስክንድር ስሜት ወስጥ አንዳች ግፊት ፈጠረበት “ ማንኛውንም መሥዋዕትነት ከፍሎ አቤልን ማዳን !” ...ግን እንዴት ? መፍትሔ ከመፈለግማ እስከ አሁንም አልቦዘነም ነበር ። “ በቅርቡ ከማርታ ጋር መተዋወቁ ምናልባት ለመፍትሔው ጥርጊያ መንገድ ይሆናል ብሎ ገመተ ። በሳምንቱ ውስጥ ከማርታ ጋር በሩቅ አንገት ከመሰበር አልፈው ሞቅ ያለ ሰላምታ መለዋወጥ ጀምረዋል።እንዲያውም ፈገግታዋ እየሞቀው ዐይኗ ወንድነቱን እየተፈታተነው በዳሌዋ ላይ በልቡ ዝቶባታል ። “ በእሷስ ድርብ ሚና ነው የምጫወተው ” ብሎ አስቧል ።
ባገኘችው ቁጥር ስለ አቤል ትጠይቀዋለች ። አቅልሎ ይመልስላታል ። ትዕግሥትንም ከእሷ ጋር ስለሚያገኛት
ሰላም ይላታል ። ሰላም ትለዋለች። ስለ አቤል ግን ጠይቃውም አታውቅም። ለአፍታ ያህልም ቢሆን ከማርታ ጋር ጨዋታ ሲያነሣ እንኳ አብራቸው አትሳተፍም ። ፈንጠር ብላ ቆማ
ትጠብቃታለች ። ይሁን እንጂ እሷም ፍቅሯን አምቃ እንደምትሠቃይ እስክንድር የሰውነቷን መክሳትና መላ አኳኃኗን በማስተዋል መገመት ችሏል መጀመሪያ ላይ ዝምታዋ አሰፈራርቶት ነበር ። በኋላ ግን አቤል በማርታ ላይ ያለውን ዐይነት መጥፎ ስሜት ትዕግሥት በእሱ በእስክንድር ላይ እንደ ሌላት ከሰሳምታ አለዋወጧ ግብቶታል ።
ታዲያ እንዴት ይደርሳል ? ብዙ ገለጻ አምልጦታል ።ሳምንት ቀላል ጊዜ አይደለም ” ሲሉ ዮናታን የጸጥታውን
አየር አደፈረሱት ።
“ እሱ እንኳ እኔ የወሰድኩትን ማስታወሻ እያነበበ ከመጻሕፍት ጋር ሲያገናዝብ ይደርስብናል ” አለና እስክንድር መናገር የፈለግወን ሳይጨርስ አንድ ነገር ራሱን
መታው ። ይህን መናገር የደፈረው የቀድሞው አቤል በጭንቅላቱ ወስጥ ስለ ተቀረጸ ነው ። በርግጥም አቤል በተለይ
የቀለም ትምህርትን ለመረዳት ፈጣን ነበር ብሩህ አእምሮ ነበረው ። አሁን ግን የብሩህ አእምሮው ዐይኖች በሆነ ነገር
ተሸፍነዋል ። የብሩህ አእምሮው ልብ በሆነ ነገር ተደፍኗል እናም እስክንድር ይህ ሐሳብ ድንገት በታየው ጊዜ ለዮናታን አጉል ቃል እንዳይገባ ፈርቶ፡ “ ብቻ እንጃ” አላቸው "በሚያመነታ ስሜት ።
“ እንዴት ? ” አሉ ዮናታን "
💥ይቀጥላል💥
በተከታታይ አልገባም ። ክፍል ውስጥ ቢጠይቁት እስክንድር የሰጣቸው መልስ " ራሱን ትንሽ ስላመመው ነው ”ብሎ ነበር : ነግር ግን ደጋግሞ መቅረቱ ከዚህ የከፋ ሁኔታ ቢያጋጥመው ነው ብለው ስላሰቡ ስለሱ ሊጠይቁት ነው የቀጠሩት።
“ ስለ አቤል ልጠይቅህ ነበር'ኮ” አሉት ዮናታን ገና ቁጭ ከማለታቸው ፡ “ በእርግጥ በጠናው ነው ? ”
እስክንድር የተጠየቀው ያው የጠበቀውን ነገር ቢሆንም ስለ አቤል መስማትም ሆነ መናገር የማይፈልግበት ወቅት ነበር ። ሁኔታው ያበሽቀዋል ። ምንም ግልጽ የሆነለት ነግር የለም ። እንደጓኝነቱ ቀርቦ ቢያዋየው ፡ አባትነት በተሞላው ሁኔታ ቢያስታምመውም ፥ ቢያሻሽውም ፡ ቢኮረኩረውም ከአቤል ጠብ ያለ ነገር የለም ። አቤል አይናገርም ።አቤል ታፍኖ መሞት የሚፈልግ ሰው ነው ።
ስለ እሱ ሊጠይቁኝ እንደሆነ ጎብቶኛል ” አለ እስክንድር በቀደም እለት ምግብ አዳራሽ ሲገባ የሆነ ነገር አደናቅፎት ወድቆ ነበር ። ያን ያህል ጉዳት እንኳ አላገኘውም ፤ግን እንጃ ! ክፍልም አልገባም አለ ተኝቶ ነው የሚውለው
የመንፈስ መረበሽ መሰለኝ ።
“ እህ ! እንዲያ ነው ? ” አሉ ዮናታን ነገሩ ልባቸውን ቢከብደውም ኀዝናቸውን ለመደበቅ ሞክረው ምን መንፈሱ የተጐዳ ሰው'ኮ ዕንቅፋትም ይበቃዋል ። ”
“ እንደዚያ ሆኖ ነው መሰለኝ ”
ዮናታን ለደቂቃ ያህል ዝም አሉ : ብዙ ነገር ሐሳባቸው ውስጥ ብዙ ነገር እየተተራመሰባቸው ነበር እስክንድር የዮናታን ስሜት ምን ያህል ጭንቀት እንዶ ተወጣጠረ ከገጽታቸው ላይ ማንበብ ችሏል ። “ ይህን ያህል ለአንድ ተማሪ መጨነቃችን ምንድነው ? ” ሲል አሰበ ። ነገር ግን የአቤል ሁኔታ እሱን ራሱን እንዳስጨነቀው ባሰበ ጊዜ ዮናታንም ተመሳሳይ ስሜት ሊያድርባቸው እንደሚችል ገመተ ። ሐቀኛ ምሁር ነኝ
የሚተካውን ጠንካራ ተማሪ በጥቃቅን ማኅበራዊ ችግር ተደናቅፎ ሲቀር ማየት አይፈልግም ።
የዮናታን ሁኔታ ፡ በእስክንድር ስሜት ወስጥ አንዳች ግፊት ፈጠረበት “ ማንኛውንም መሥዋዕትነት ከፍሎ አቤልን ማዳን !” ...ግን እንዴት ? መፍትሔ ከመፈለግማ እስከ አሁንም አልቦዘነም ነበር ። “ በቅርቡ ከማርታ ጋር መተዋወቁ ምናልባት ለመፍትሔው ጥርጊያ መንገድ ይሆናል ብሎ ገመተ ። በሳምንቱ ውስጥ ከማርታ ጋር በሩቅ አንገት ከመሰበር አልፈው ሞቅ ያለ ሰላምታ መለዋወጥ ጀምረዋል።እንዲያውም ፈገግታዋ እየሞቀው ዐይኗ ወንድነቱን እየተፈታተነው በዳሌዋ ላይ በልቡ ዝቶባታል ። “ በእሷስ ድርብ ሚና ነው የምጫወተው ” ብሎ አስቧል ።
ባገኘችው ቁጥር ስለ አቤል ትጠይቀዋለች ። አቅልሎ ይመልስላታል ። ትዕግሥትንም ከእሷ ጋር ስለሚያገኛት
ሰላም ይላታል ። ሰላም ትለዋለች። ስለ አቤል ግን ጠይቃውም አታውቅም። ለአፍታ ያህልም ቢሆን ከማርታ ጋር ጨዋታ ሲያነሣ እንኳ አብራቸው አትሳተፍም ። ፈንጠር ብላ ቆማ
ትጠብቃታለች ። ይሁን እንጂ እሷም ፍቅሯን አምቃ እንደምትሠቃይ እስክንድር የሰውነቷን መክሳትና መላ አኳኃኗን በማስተዋል መገመት ችሏል መጀመሪያ ላይ ዝምታዋ አሰፈራርቶት ነበር ። በኋላ ግን አቤል በማርታ ላይ ያለውን ዐይነት መጥፎ ስሜት ትዕግሥት በእሱ በእስክንድር ላይ እንደ ሌላት ከሰሳምታ አለዋወጧ ግብቶታል ።
ታዲያ እንዴት ይደርሳል ? ብዙ ገለጻ አምልጦታል ።ሳምንት ቀላል ጊዜ አይደለም ” ሲሉ ዮናታን የጸጥታውን
አየር አደፈረሱት ።
“ እሱ እንኳ እኔ የወሰድኩትን ማስታወሻ እያነበበ ከመጻሕፍት ጋር ሲያገናዝብ ይደርስብናል ” አለና እስክንድር መናገር የፈለግወን ሳይጨርስ አንድ ነገር ራሱን
መታው ። ይህን መናገር የደፈረው የቀድሞው አቤል በጭንቅላቱ ወስጥ ስለ ተቀረጸ ነው ። በርግጥም አቤል በተለይ
የቀለም ትምህርትን ለመረዳት ፈጣን ነበር ብሩህ አእምሮ ነበረው ። አሁን ግን የብሩህ አእምሮው ዐይኖች በሆነ ነገር
ተሸፍነዋል ። የብሩህ አእምሮው ልብ በሆነ ነገር ተደፍኗል እናም እስክንድር ይህ ሐሳብ ድንገት በታየው ጊዜ ለዮናታን አጉል ቃል እንዳይገባ ፈርቶ፡ “ ብቻ እንጃ” አላቸው "በሚያመነታ ስሜት ።
“ እንዴት ? ” አሉ ዮናታን "
💥ይቀጥላል💥
#የታካሚው_ማስታወሻ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
“ጨዋታ እንቀይር፡፡ በሀይማኖት ተከራክሮ፣ መቀያየም ካልሆነ መተማመን ማይታሰብ ነው፡፡”
“እሺ! ደስ እንዳለህ፡፡ ግን ሳስብህ ልብህ በውጪው ባህል የሸፈተ ይመስላል፡፡ ሚስትህ ፈረንጅ ነች እንዴ...?”
“ኧረ ሚስት የለኝም፡፡”
“ሚስትም ባይሆን ፍቅረኛ፡፡”
“ፍቅረኛም የለኝም፡፡”
“እሺ፣ ፈረንጅ ጠብሰህ ታውቃለህ?” ያን ፈገግታዋን ፍልቅቅ አደረገችልኝ፡፡
“እንደሱማ፣ አንድ ሁለቴ አይጠፋም፡፡”
“እውነት..?! ምናቸው ደስ ብሎህ?
ከአበሻ እንዴት በለጡብህ?”
ፊቷን ኮሶ እንደሚጠጣ ሰው ከስክሳ አከታትላ ጠየቀችኝ፡፡
“እንደኔ እብድ ናቸው፡፡ ከፈለጉሽ እራሳቸው ይጠብሱሻል፡፡ አስር
ገሰስ አያበዙም፡፡”
“እራሳቸው ይጠብሳሉ? እንደሱ አጋጥሞህ ያውቃል? በናትህ
ንገረኝ?” እንዳወራት ፍልቅልቅ ፈገግታዋን ቀብድ ከፈለችኝ፡፡
“እሺ፡፡ አንዴ አብራኝ የምትስራ ባልደረባ
ነበረችኝ፡፡ እንቀራረባለን፡፡”
“እሺ...”
“አብረን እንሰራለን፤ አብረን እንበላለን፡፡ አንድ ቀን፣ አስቸኳይ ስራ እየሰራን፣ ምሳ ደረሰ፡፡ እራበን፡፡ ስራው አሰቸኳይ ስለነበር ላፕቶፑን ይዘን እየሰራን ምሳ ልንበላ ወጣን፡፡”
“እሺ..”
እየሰራን ምሳ መጣ፡፡ እኔ እየበላሁ ሃሳብ አዋጣለሁ፡፡ እርሷ እየፃፈች አልፎ አልፎ ትጎርሳለች፡፡ ትንሽ እንደበላን፤
'አበሻ ጥሩ ባህል አለው፤ አለችኝ ::
ምንድን ነው እሱ?” አልኳት፡፡
ሲበላ ይጎራረሳል፡፡ አለችኝ፡፡
በአሽሙሯ በጣም ተገርሜ ሳቅኩና አጎርሳት ጀመር፡፡ ሳጎርሳት ሆን ብላ፣ ጣቶቼንም በስስ ከንፈሮቿ ላሰቻቸው፡፡ ቀና ብዬ ሳያት፣በመሽኮርመም ፈገግ አለች፡፡ የሆነ አዲስ ስሜት ወረረኝ፡፡ ከስራ
ባልደረባነቷ በተለየ፣ በሌላ ስሜት አሰብኳት፡፡ ማታ አስቸኳይ ስራውን
ስለጨረስን፣ እናክብረው፣ ልጋብዝህ አለችኝና ሞቅ እስኪለን ስንጠጣ፣
ስንጫወት፣ ስንስቅ አመሸን፡፡ ሲመሽ መኪናዋ ድረስ ሸኘኋት፡፡ እንድገባ ጋበዘችኝ፡፡ ገባሁ፤ ሳታስፈቅደኝ ትስመኝ ጀመር፡፡ አለተቃወምኳትም፡፡በቃ ተጀመረ፡ ከዛ ቀን በኋላ፣ ዛሬኮ የደሞዝ ቀን ነው፣ አርብ ነው፣ ደብሮናል፣ ብዙ ስራ ሰርተናል...፣ ተያይዞ መውጣት ሆነ፡፡”
“እብድ ነህ፡፡”
“አንዳንዴ አዎ፡፡ ግን፣ ሁሌም እብድ ብሆን ደስ ይለኛል፡፡”
“ማለት?”
“ደስ ደስ የሚሉ ነገሮችን የምሰራው፣ እብድ ስሆን ነዋ፡፡ ያለበለዛ ይሰለቸኛል፤ ያስጠላኛል፤ ውስጤ ይጠወልጋል፤ የመኖር ለዛው ይጠፋብኛል፡፡”
“ሆ ...፣ ቆይ አሁን እብድ ነህ...?” ሳቀችብኝ፡፡
“ሃ...ሃ...ሃ.... በጣም አታስቂኝ፤ ልትሸሺኝ ነው?” ድንገት ንዴት ተሰማኝ፡፡
“እና...፣ አስፈራራኸኝ እኮ፡፡” ይባስ ተበሳጨሁ። የተማረች አንባቢ ብዬ አፌን የከፈትኩላት፣ ቀልድ ማይገባት እንጭጭ ነች፡፡
“አታስቢ እናቱ፣ እኔው ቀድሜ እሸሽሻለሁ፡፡”
“ኧረ ባክህ?” አለችኝ፡፡
አልመለስኩላትም፡፡ ወደ ውስጤ ተወሸኩኝ፡፡ ባወራሁላት ነገር ማንነቴን የገመተችኝ መስሎ ተሰማኝ፡፡ እየቆየ በጣም እየተናደድኩና እየተበሳጨሁ መጣሁ፡፡ በዝምታዬ ውስጥ ንዴቴ ይንቀለቀል ጀመር፡፡ዝምታዬ ያሰፈራል። ደንግጣ ፀጥ አለች፡፡ ወሬ ጠፋባት፡፡ ልጅቷ በአንዴ አስጠላችኝ፡፡ እረጅም መንገድ በፀጥታ ተጓዝን፡፡ አስራ ሁለት ሰዐት አልፎ ለዐይን ያዝ ማድረግ ጀምሯል፡፡ እንደዛ ልቤንና ውስጤን ያቆመ
ውበቷ፣ እንደጉም በኖ ጠፋ። ማርቆስ ደረስን፡፡
“እንቺ መፅሃፍሽን!” አልኳት፡፡
“ስጦታዬ ነው፣ አንብበው፡፡”
“አመሰግናለሁ! ገዝቼ አነበዋለሁ፤ ስጦታሽ አያስፈልገኝም፡፡” ብዬ መፅሃፉን ገፈተርኩላት፡፡
“ቆይ ምንድን ነው ያስቀየምኩህ?
በአንዴ እንዲህ የተለወጥከው፡፡”
“ምንም አላጠፋሽም፡፡ ፈልጌው ነው፡፡”
“ኧረ ይደብራል፡፡ እሺ ካስቀየምኩህ ይቅርታ!”
“አላስቀየምሽኝም፡፡ ይቅርታም አያስፈልግም፡፡”
መኪናው ሰው ለማውረድ ቆመ፡፡ አሳልፊኝ ብዬ፣ ገፈታትሪያት ልወርድ ስል፣ መኪናው ተመልሶ ሲንቀሳቀስ፣ በጀርባዬ ልደፋ ስል፣ ከኋላ ደገፈችኝ፡፡ መንጭቂያት፣ በራሴ እንደቆመ ሆንኩኝ፡፡
ሰዉ “ኧረ ቆይ ወራጅ አለ!” ብሎ ጮኸ፡፡
“ዐይን የለህም?፣ ወራጅ እየወረደ ምትነዳው? መሃይም” አምባረኩበት፡፡
“የወረደው ሰውዬ ነው፣ ወራጅ ያለኝ፤” አለ እረዳቱ፣ በሩን እየከፈተልኝ፡፡
“እና፣ ዞር ብለህ አታይም! ደደብ! እዚህ የማንም መሃይም ከየትም መንጃ ፍቃድ ይለቃቅምና፣ ስለሰው ደንታ የላቸውም፡፡”
እየተሳደብኩ ወረድኩ፡፡
በአንዴ፣ እንዲህ ምን እንዳበሳጨኝ እኔም እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ሰሞኑን፣ በትንሽ ነገር እናደድና ቀስ በቀስ ብስጭቴ
ከመጠን ያለፈ ይሆናል፡፡ ያናደደኝን በቅጡ ይሄ ነው ብዬ መለየት እስከማልችል ድረስ፡፡ የቀባጠርኩላት ደጋግሞ ወደ ጭንቅላቴ እየመጣ፣
ስህተት ነበርክ፤ ቀሽም ነህ፤ በነገረካት ደካማ ጎንህ አላገጠችብህ፤” እያለ
ይነዘንዘኛል፡፡ ከለቀቀኝ ብዬ አልጋ ይዤ ሻወር ወሰድኩ፡፡ ለውጥ የለም፡፡
ሃሳቦቹ እንደ ንፋስ ውልብ እያሉ መጥፎ ስሜት ይለቁብኛል፡፡ በመጠጥ
ለመደበቅ ወሰንኩኝ፡፡ እራቴን በልቼ፣ ንዴቴና ብስጭቴ እስኪጠፋ፣ እስክስክርና እስክደነዝዝ፣ ድረስ፣ መጠጦችን እየቀያርኩ ስጠጣ አደርኩ፡፡
በንጋታው አረፋፍጄ ባህር ዳር ምሳ በልቼ ጎንደር ገብቼ አደረኩ፡፡
ጉዞ ወደ መተማ ዮሀንስ
መተማ ለመሄድ፣ ከጎንደር አዘዞ መናኸሪያ ሚኒባስ ተሳፈርኩኝ፡፡ ሚኒባሱ ወደ መሙላቱ ነው፡፡ አብዛኛው መኪናው ላይ የተሳፈሩት ወጣቶች ናቸው፡፡ ከአጠገቤ የተቀመጠው ወጣት እድሜው
በግምት ስላሳ አካባቢ ይሆናል፡፡የለበሰው ልብስ ወይቧል፡፡ ከተማ ቀመስ ይመስላል በመስኮት አጠገብ ለመቀመጥ ቦታ እንዲቀይረኝ ጠየኩት።ሳያቅማማ ቦታውን ቀየረኝ፡፡ ታክሲው እስክንተፋፈግ ድረስ ትርፍ ጭኖ መንገድ ጀመረ፡፡ የያዝኩት ገንዘብ፣ በየቀኑ እየሳሳ፣ እየመነመነ፣ አሁን ያሳሰበኝ ጀምሯል፡፡ አሁን ሃሳቤን ብቀይር እንኳ፣ መልሼ መቋቋም
ማልችልበት ደረጃ ደርሻለሁ፡፡ መፍጠን አለብኝ፡፡ መተፋፈጉን ለመርሳት፣ በመኪናው መስኮት አሻግሬ ሃሳብ የሚይዝ ነገር ፍለጋ ዐይኔን ላኩት፡፡ ምንም ቀልብ ሚይዝ ሚታይ ነገር የለም፡፡
ግማሽ መንገድ እንደሄድን ታክሲው ቆመ፡፡ ሾፌሩ የአርሴማን በረከት መያዝ የምትፈልጉ ሃያ ደቂቃ ብሎ ወረደ፡፡ ተሳፋሪው በሙሉ ተከተለው፡፡ ህብስት ዳቦ፣ ብርቱካን፣ ማንጎ፣ ይዘው የሚሸጡ ወጣቶች፣
የቅድስት አርሴማ በረከት እያሉ በመስኮት በኩል ያሳዩኛል። በቀኝ በኩል ተደርድረው የተሰሩ የጭቃ ቤቶች ይታያሉ፡፡እንደሱቅና ካፍቴሪያ እየሰሩ ነው፡፡ በስተግራ በደን የተሸፈነ ተራራ ይታያል፡፡ ከተራራው ስር
ምንጮች ይፈሳሉ፡፡ ሰዎች ተሰባስበው በምንጮቹ ውሃ ልብስ ያጥባሉ፡፡
ውሃ በጀሪካን ይቀዳሉ፡፡ ተራራው ጫፍ ላይ ትልቅ የተሰቀላ መስቀል በርቀት ይታያል፡፡ ተሳፋሪዎች፣ ህብስት ዳቦ እየበሉ፣ የገዟቸውን በረከቶች በፌስታል ጠቅልለው ገቡ፡፡ ሹፌሩ የቀረ ሰው እንደሌለ ካረጋገጠ በኋላ ጉዞውን ቀጠለ፡፡
አጠገቤ የተቀመጠው ልጅ፣ “ስለቅድስት አርሴማ!” ብሎ ህብስት ዳቦ ወደ እኔ ዘረጋልኝ፡፡ትንሽ ቆንጥሬ አርሴማ ትስጥልኝ አልኩት፡፡እስካሁን እንዳያወራኝ መንገድ ስዘጋበት ነበር፡፡ ሰሞኑን ድብርቴ ከፍተኛ ደረጃ ደርሷል፡፡ ማንንም ማናገር አስጠልቶኛል፡፡ ምግብና መጠጥ ሳዝ
እንኳ መመላለስ ሰልችቶኛል፡፡ላለመነጋገር፣ ያዘዝኩትን እንኳ ቀይረው
ሲያመጡልኝ፣ ንዴቴን ውጩ፣ ያመጡልኝን እጠቀማለሁ፡፡ ግን አሁን የቆምንበትን ምክንያት ማወቅ ፈለኩኝ፡፡
አጠገቤ የተቀመጠውን ወጣት “ለምንድነው የቆምነው?” ብዬ
ጠየኩት፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
“ጨዋታ እንቀይር፡፡ በሀይማኖት ተከራክሮ፣ መቀያየም ካልሆነ መተማመን ማይታሰብ ነው፡፡”
“እሺ! ደስ እንዳለህ፡፡ ግን ሳስብህ ልብህ በውጪው ባህል የሸፈተ ይመስላል፡፡ ሚስትህ ፈረንጅ ነች እንዴ...?”
“ኧረ ሚስት የለኝም፡፡”
“ሚስትም ባይሆን ፍቅረኛ፡፡”
“ፍቅረኛም የለኝም፡፡”
“እሺ፣ ፈረንጅ ጠብሰህ ታውቃለህ?” ያን ፈገግታዋን ፍልቅቅ አደረገችልኝ፡፡
“እንደሱማ፣ አንድ ሁለቴ አይጠፋም፡፡”
“እውነት..?! ምናቸው ደስ ብሎህ?
ከአበሻ እንዴት በለጡብህ?”
ፊቷን ኮሶ እንደሚጠጣ ሰው ከስክሳ አከታትላ ጠየቀችኝ፡፡
“እንደኔ እብድ ናቸው፡፡ ከፈለጉሽ እራሳቸው ይጠብሱሻል፡፡ አስር
ገሰስ አያበዙም፡፡”
“እራሳቸው ይጠብሳሉ? እንደሱ አጋጥሞህ ያውቃል? በናትህ
ንገረኝ?” እንዳወራት ፍልቅልቅ ፈገግታዋን ቀብድ ከፈለችኝ፡፡
“እሺ፡፡ አንዴ አብራኝ የምትስራ ባልደረባ
ነበረችኝ፡፡ እንቀራረባለን፡፡”
“እሺ...”
“አብረን እንሰራለን፤ አብረን እንበላለን፡፡ አንድ ቀን፣ አስቸኳይ ስራ እየሰራን፣ ምሳ ደረሰ፡፡ እራበን፡፡ ስራው አሰቸኳይ ስለነበር ላፕቶፑን ይዘን እየሰራን ምሳ ልንበላ ወጣን፡፡”
“እሺ..”
እየሰራን ምሳ መጣ፡፡ እኔ እየበላሁ ሃሳብ አዋጣለሁ፡፡ እርሷ እየፃፈች አልፎ አልፎ ትጎርሳለች፡፡ ትንሽ እንደበላን፤
'አበሻ ጥሩ ባህል አለው፤ አለችኝ ::
ምንድን ነው እሱ?” አልኳት፡፡
ሲበላ ይጎራረሳል፡፡ አለችኝ፡፡
በአሽሙሯ በጣም ተገርሜ ሳቅኩና አጎርሳት ጀመር፡፡ ሳጎርሳት ሆን ብላ፣ ጣቶቼንም በስስ ከንፈሮቿ ላሰቻቸው፡፡ ቀና ብዬ ሳያት፣በመሽኮርመም ፈገግ አለች፡፡ የሆነ አዲስ ስሜት ወረረኝ፡፡ ከስራ
ባልደረባነቷ በተለየ፣ በሌላ ስሜት አሰብኳት፡፡ ማታ አስቸኳይ ስራውን
ስለጨረስን፣ እናክብረው፣ ልጋብዝህ አለችኝና ሞቅ እስኪለን ስንጠጣ፣
ስንጫወት፣ ስንስቅ አመሸን፡፡ ሲመሽ መኪናዋ ድረስ ሸኘኋት፡፡ እንድገባ ጋበዘችኝ፡፡ ገባሁ፤ ሳታስፈቅደኝ ትስመኝ ጀመር፡፡ አለተቃወምኳትም፡፡በቃ ተጀመረ፡ ከዛ ቀን በኋላ፣ ዛሬኮ የደሞዝ ቀን ነው፣ አርብ ነው፣ ደብሮናል፣ ብዙ ስራ ሰርተናል...፣ ተያይዞ መውጣት ሆነ፡፡”
“እብድ ነህ፡፡”
“አንዳንዴ አዎ፡፡ ግን፣ ሁሌም እብድ ብሆን ደስ ይለኛል፡፡”
“ማለት?”
“ደስ ደስ የሚሉ ነገሮችን የምሰራው፣ እብድ ስሆን ነዋ፡፡ ያለበለዛ ይሰለቸኛል፤ ያስጠላኛል፤ ውስጤ ይጠወልጋል፤ የመኖር ለዛው ይጠፋብኛል፡፡”
“ሆ ...፣ ቆይ አሁን እብድ ነህ...?” ሳቀችብኝ፡፡
“ሃ...ሃ...ሃ.... በጣም አታስቂኝ፤ ልትሸሺኝ ነው?” ድንገት ንዴት ተሰማኝ፡፡
“እና...፣ አስፈራራኸኝ እኮ፡፡” ይባስ ተበሳጨሁ። የተማረች አንባቢ ብዬ አፌን የከፈትኩላት፣ ቀልድ ማይገባት እንጭጭ ነች፡፡
“አታስቢ እናቱ፣ እኔው ቀድሜ እሸሽሻለሁ፡፡”
“ኧረ ባክህ?” አለችኝ፡፡
አልመለስኩላትም፡፡ ወደ ውስጤ ተወሸኩኝ፡፡ ባወራሁላት ነገር ማንነቴን የገመተችኝ መስሎ ተሰማኝ፡፡ እየቆየ በጣም እየተናደድኩና እየተበሳጨሁ መጣሁ፡፡ በዝምታዬ ውስጥ ንዴቴ ይንቀለቀል ጀመር፡፡ዝምታዬ ያሰፈራል። ደንግጣ ፀጥ አለች፡፡ ወሬ ጠፋባት፡፡ ልጅቷ በአንዴ አስጠላችኝ፡፡ እረጅም መንገድ በፀጥታ ተጓዝን፡፡ አስራ ሁለት ሰዐት አልፎ ለዐይን ያዝ ማድረግ ጀምሯል፡፡ እንደዛ ልቤንና ውስጤን ያቆመ
ውበቷ፣ እንደጉም በኖ ጠፋ። ማርቆስ ደረስን፡፡
“እንቺ መፅሃፍሽን!” አልኳት፡፡
“ስጦታዬ ነው፣ አንብበው፡፡”
“አመሰግናለሁ! ገዝቼ አነበዋለሁ፤ ስጦታሽ አያስፈልገኝም፡፡” ብዬ መፅሃፉን ገፈተርኩላት፡፡
“ቆይ ምንድን ነው ያስቀየምኩህ?
በአንዴ እንዲህ የተለወጥከው፡፡”
“ምንም አላጠፋሽም፡፡ ፈልጌው ነው፡፡”
“ኧረ ይደብራል፡፡ እሺ ካስቀየምኩህ ይቅርታ!”
“አላስቀየምሽኝም፡፡ ይቅርታም አያስፈልግም፡፡”
መኪናው ሰው ለማውረድ ቆመ፡፡ አሳልፊኝ ብዬ፣ ገፈታትሪያት ልወርድ ስል፣ መኪናው ተመልሶ ሲንቀሳቀስ፣ በጀርባዬ ልደፋ ስል፣ ከኋላ ደገፈችኝ፡፡ መንጭቂያት፣ በራሴ እንደቆመ ሆንኩኝ፡፡
ሰዉ “ኧረ ቆይ ወራጅ አለ!” ብሎ ጮኸ፡፡
“ዐይን የለህም?፣ ወራጅ እየወረደ ምትነዳው? መሃይም” አምባረኩበት፡፡
“የወረደው ሰውዬ ነው፣ ወራጅ ያለኝ፤” አለ እረዳቱ፣ በሩን እየከፈተልኝ፡፡
“እና፣ ዞር ብለህ አታይም! ደደብ! እዚህ የማንም መሃይም ከየትም መንጃ ፍቃድ ይለቃቅምና፣ ስለሰው ደንታ የላቸውም፡፡”
እየተሳደብኩ ወረድኩ፡፡
በአንዴ፣ እንዲህ ምን እንዳበሳጨኝ እኔም እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ሰሞኑን፣ በትንሽ ነገር እናደድና ቀስ በቀስ ብስጭቴ
ከመጠን ያለፈ ይሆናል፡፡ ያናደደኝን በቅጡ ይሄ ነው ብዬ መለየት እስከማልችል ድረስ፡፡ የቀባጠርኩላት ደጋግሞ ወደ ጭንቅላቴ እየመጣ፣
ስህተት ነበርክ፤ ቀሽም ነህ፤ በነገረካት ደካማ ጎንህ አላገጠችብህ፤” እያለ
ይነዘንዘኛል፡፡ ከለቀቀኝ ብዬ አልጋ ይዤ ሻወር ወሰድኩ፡፡ ለውጥ የለም፡፡
ሃሳቦቹ እንደ ንፋስ ውልብ እያሉ መጥፎ ስሜት ይለቁብኛል፡፡ በመጠጥ
ለመደበቅ ወሰንኩኝ፡፡ እራቴን በልቼ፣ ንዴቴና ብስጭቴ እስኪጠፋ፣ እስክስክርና እስክደነዝዝ፣ ድረስ፣ መጠጦችን እየቀያርኩ ስጠጣ አደርኩ፡፡
በንጋታው አረፋፍጄ ባህር ዳር ምሳ በልቼ ጎንደር ገብቼ አደረኩ፡፡
ጉዞ ወደ መተማ ዮሀንስ
መተማ ለመሄድ፣ ከጎንደር አዘዞ መናኸሪያ ሚኒባስ ተሳፈርኩኝ፡፡ ሚኒባሱ ወደ መሙላቱ ነው፡፡ አብዛኛው መኪናው ላይ የተሳፈሩት ወጣቶች ናቸው፡፡ ከአጠገቤ የተቀመጠው ወጣት እድሜው
በግምት ስላሳ አካባቢ ይሆናል፡፡የለበሰው ልብስ ወይቧል፡፡ ከተማ ቀመስ ይመስላል በመስኮት አጠገብ ለመቀመጥ ቦታ እንዲቀይረኝ ጠየኩት።ሳያቅማማ ቦታውን ቀየረኝ፡፡ ታክሲው እስክንተፋፈግ ድረስ ትርፍ ጭኖ መንገድ ጀመረ፡፡ የያዝኩት ገንዘብ፣ በየቀኑ እየሳሳ፣ እየመነመነ፣ አሁን ያሳሰበኝ ጀምሯል፡፡ አሁን ሃሳቤን ብቀይር እንኳ፣ መልሼ መቋቋም
ማልችልበት ደረጃ ደርሻለሁ፡፡ መፍጠን አለብኝ፡፡ መተፋፈጉን ለመርሳት፣ በመኪናው መስኮት አሻግሬ ሃሳብ የሚይዝ ነገር ፍለጋ ዐይኔን ላኩት፡፡ ምንም ቀልብ ሚይዝ ሚታይ ነገር የለም፡፡
ግማሽ መንገድ እንደሄድን ታክሲው ቆመ፡፡ ሾፌሩ የአርሴማን በረከት መያዝ የምትፈልጉ ሃያ ደቂቃ ብሎ ወረደ፡፡ ተሳፋሪው በሙሉ ተከተለው፡፡ ህብስት ዳቦ፣ ብርቱካን፣ ማንጎ፣ ይዘው የሚሸጡ ወጣቶች፣
የቅድስት አርሴማ በረከት እያሉ በመስኮት በኩል ያሳዩኛል። በቀኝ በኩል ተደርድረው የተሰሩ የጭቃ ቤቶች ይታያሉ፡፡እንደሱቅና ካፍቴሪያ እየሰሩ ነው፡፡ በስተግራ በደን የተሸፈነ ተራራ ይታያል፡፡ ከተራራው ስር
ምንጮች ይፈሳሉ፡፡ ሰዎች ተሰባስበው በምንጮቹ ውሃ ልብስ ያጥባሉ፡፡
ውሃ በጀሪካን ይቀዳሉ፡፡ ተራራው ጫፍ ላይ ትልቅ የተሰቀላ መስቀል በርቀት ይታያል፡፡ ተሳፋሪዎች፣ ህብስት ዳቦ እየበሉ፣ የገዟቸውን በረከቶች በፌስታል ጠቅልለው ገቡ፡፡ ሹፌሩ የቀረ ሰው እንደሌለ ካረጋገጠ በኋላ ጉዞውን ቀጠለ፡፡
አጠገቤ የተቀመጠው ልጅ፣ “ስለቅድስት አርሴማ!” ብሎ ህብስት ዳቦ ወደ እኔ ዘረጋልኝ፡፡ትንሽ ቆንጥሬ አርሴማ ትስጥልኝ አልኩት፡፡እስካሁን እንዳያወራኝ መንገድ ስዘጋበት ነበር፡፡ ሰሞኑን ድብርቴ ከፍተኛ ደረጃ ደርሷል፡፡ ማንንም ማናገር አስጠልቶኛል፡፡ ምግብና መጠጥ ሳዝ
እንኳ መመላለስ ሰልችቶኛል፡፡ላለመነጋገር፣ ያዘዝኩትን እንኳ ቀይረው
ሲያመጡልኝ፣ ንዴቴን ውጩ፣ ያመጡልኝን እጠቀማለሁ፡፡ ግን አሁን የቆምንበትን ምክንያት ማወቅ ፈለኩኝ፡፡
አጠገቤ የተቀመጠውን ወጣት “ለምንድነው የቆምነው?” ብዬ
ጠየኩት፡፡
👍2❤1
በግራ በኩል ያለው ተራራ፣ የቅድስት አርሴማ ገዳም ነው፡፡በጣም ተአምረኛ ገዳም ነው፡፡ ከበረከቱ ለመሳተፍ ነው፤” አለኝ፡፡
ስለ ቅድስት አርሴማ ሰምቼ አላውቅም፡፡ ምንድነው ታሪኳ?”
ቅድስት አርሴማ አርመናዊ ቅድስት ነች። በዚህ ምድር ያለው መከራና ስቃይ፣ ሰይጣንና እግዚአብሄር ቢታረቁ ይፈታል ብላ ስለምታምን፣ ሁለቱን ልታስታርቅ የፀለየች ቅድስት ናት፤” አለኝ፡፡
መኪናው እየሄደ ነው፡፡ በመስኮቴ ወደኋላ ዞሬ፣ ገዳሙን ከጀርባ በኩል አየሁት፡፡ ከጀርባ፣ ተራራው ቀጥ ያለ ነው፡፡ የገዳሙ ጀርባ እንደ ፊት ለፊቱ ለምለምና አረንጓዴ ሳይሆን፣ በረሀና ገደላማ ነው፡፡ ትልቁ
የብረት መስቀል አሁንም ከርቀት ይታየኛል፡፡
“የቆየ ገዳም ነው” ብዬ ጠየኩት፡፡
“አስር ዓመት አካባቢ ይሆነዋል፡፡ ግን፣ አርሴማ ፀሎት ቶሎ ስለምትሰማ ብዙ ሰው ይመጣል።”
“ጥሩ ነው፡፡”
“ከአዲስ አበባ ነህ?”
“አዎ፡፡ እንዴት አወቅክ?”
“እዚህ አካባቢ ይህን ገዳሙን ማያውቀው የለም ብዬ ነው።”
“ለስራ ነው ሁመራ የምትሄደው?” ጀመረኝ፡፡
“አዎ፡፡”...
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ስለ ቅድስት አርሴማ ሰምቼ አላውቅም፡፡ ምንድነው ታሪኳ?”
ቅድስት አርሴማ አርመናዊ ቅድስት ነች። በዚህ ምድር ያለው መከራና ስቃይ፣ ሰይጣንና እግዚአብሄር ቢታረቁ ይፈታል ብላ ስለምታምን፣ ሁለቱን ልታስታርቅ የፀለየች ቅድስት ናት፤” አለኝ፡፡
መኪናው እየሄደ ነው፡፡ በመስኮቴ ወደኋላ ዞሬ፣ ገዳሙን ከጀርባ በኩል አየሁት፡፡ ከጀርባ፣ ተራራው ቀጥ ያለ ነው፡፡ የገዳሙ ጀርባ እንደ ፊት ለፊቱ ለምለምና አረንጓዴ ሳይሆን፣ በረሀና ገደላማ ነው፡፡ ትልቁ
የብረት መስቀል አሁንም ከርቀት ይታየኛል፡፡
“የቆየ ገዳም ነው” ብዬ ጠየኩት፡፡
“አስር ዓመት አካባቢ ይሆነዋል፡፡ ግን፣ አርሴማ ፀሎት ቶሎ ስለምትሰማ ብዙ ሰው ይመጣል።”
“ጥሩ ነው፡፡”
“ከአዲስ አበባ ነህ?”
“አዎ፡፡ እንዴት አወቅክ?”
“እዚህ አካባቢ ይህን ገዳሙን ማያውቀው የለም ብዬ ነው።”
“ለስራ ነው ሁመራ የምትሄደው?” ጀመረኝ፡፡
“አዎ፡፡”...
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1🔥1
#ሰመመን
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
...ማለቴ በአሁኑ ጊዜ እንኳ ሳምንት ወደኋል የቀረባችውን የትምህርት ዐይነቶች ለማሟላት ብዙ መጽሐፍ ያገላብጣል ብዬ ቃል መግባቱ ያስፈራኛል ” አላቸው ።
ዮናታን ነገሩ ስለገባቸው ደብዛዛ ፈገግታ አሳዩ ። ግን ብዙም ሳይቆዩ ፈገግታው ጭልም ብሎ ጠፍቶ ፊታቸው ተለዋወጠ ግንባራቸው ላይ ትልቅ የደምሥር ተምዘግዝጎ ወጣ ፤ ቅጽበታዊ ውሳኔ ከአእምሮአቸው ታዞ ምላሳቸውጋ
ደርሶ ነበር ።
ቃላቱን ከመወርወራቸው በፊት ያለምክንያት መነጽ ራቸውን አወለቁ ። እንደ ወትሮአቸው ዐይናቸውን ሳያሹ
መልሰው አደረጉት ። ወደ ኋላቸው ተለጥጠው ተቀመጡ ።እናም ተነፈሱ ።
ይህን ዓመት ትምህርቱን ማቋረጥ ይኖርበታል በኔ ግምት ።
እስክንድር ግር አለው፤ዝም ብሎ እያያቸው “ እና በምን ዐይነት መንገድ ልንመክረው እንችላለን ? አለ በልቡ ።
“ ምን ዐይነትምክር ነው ትምህርትን አቋርጥ ብሎ ምክር?”
“እህሳ ምነው ዝም አልክ?” አሉት ።
ትንሽ ሲያመነታ ቆየና ። “ ግን ይህችን ዓመት እንደ ምንም ጨርሶ ቢገላገል አይሻልም ? ” አላቸው ።
“ ትምህርት የሚገላገሉት ዕዳ ነው እንዴ ? ”
ማለቴ ” አለ እስክንድር ሐሳባቸው ስለ ገባው ቶሎ ብሎ በማደናገር ዐይነት ። “ ሌላ ዓመት መጨመሩ ራሱ የበለጠ ሊረብሽው ይችላል ብዬ ነው፤ ጓደኞቹ ሥራ ይዘው ሲያይ ይሄ ጊዜያዊ ሁኔታ ነው ጊዜያዊ ችግር ነው ። እኔ የማስበው ግን ከዘላቂ ሕይወቱ አንጻር ነው ። በእኔ ግምት አቤል ከጤናማ አእምሮው ጋር መመረቅ አለበት ። ከዚያ በኋላ ሥራ ይዞ ገንዘብ ማግኘት ሳይሆን ለዓለም አንድ ነገር ማበርከት ይሆናል ሕልሙ ” አሉና ዮናታን ከመጽሐፍ መደርደሪያቸው ላይ እንድ ጥራዝ አንሥተው አቤል በድጋሚ ሠርቶ የሰጣቸው የጥናት ጽሑፍ ነበር
«« ይኸውልህ ” አሉት። የጽሑፉን መግቢያ ዐልፈው መሐል ገጾቹን እያሳዩትጨ “ ከዚህ እስከዚህ ያለው ጽሑፍ የተቀዳው “ አንቲ ዱሪንግ” ከሚለው የኤንግልስ መጽሐፍ ውስጥ ነው ። ሐሳቡን ማለቴ እንዳይመስልህ! ፤ አረፍተ ነገሩ ቀርቶ ቃላቱን እንኳ አልቀየረውም ፡ ከመሰላቸትም አልፎ ትምህርቱን የመጥላት ምልክት ነው አቤል እንዲህ ዐይነት ተማሪ አልነበረም እንዳለች ከመጽሐፍ ቀድቶ ማምጣት ቀርቶ ታላላቅ ምሁራን በደረሱዋቸው ታላላቅ ሥራዎች ላይ የሚያቀርበውን ሐሳብ ለመፍታት እንኳ ያስቸግር ነበር ። አምና በአንዲት ዲያሎግ ሽንጡን ገትሮ ይዞን አስራ አምስት ቀን ሙሉ እንዳንጫጫን ትዝ፤ አይልህም ? !እኔ ያኔ እሱ ባነሣት ጥያቄ የራሱን ምሁራዊ ብቁነት ተጠራጥሬ እንደገና መጻሕፍት ሳገላብጥ የከረምኩብት ጊዜ ነበር ።
አሁን ግን የዚያን ጊዜው አቤል አይደለም ችሎታው አለው ። ግን አንዳች ችግር ደርሶበታል ። ስለዚህ ችግሩ ከተገለጠ በኋላ ነው ትምህርቱን በሚገባ ሊያጠናቅቅ የሚችለው እንጂ አድበስብሰው ቢያሳልፉት ምንም ጥቅም
የለውም።
እስክንድር የጥናት ጽሑፉን ወረቀት እያየ ፈዞ ቀረ ።እንዳለ የመፀፉ ግልባጭ ነበር አቤል ይህን የጥናት አርስት ወስዶ እንደገና እንዲሰራ ዮናታን በመከሩት ጊዜ መልሶ ወስዶ ሲያምጥበት ዐሥራ አምስት ቀን ያህል አስቀመጠው ። በመጨረሻም ከጠቀሱት መጽሐፍ ውስጥ እንዳለ ገልብጦ ሰጣቸው አያውቁም ብሎ አልነበረም ይህን ያረገው ከእጁ እንዲወጣለት ብቻ እንጂ ።
“ እና አሁን ትምህርቱን እርም ብሎ ከመተዉ በፊት እንዲያቋርጥ በዘዴ ብንመክረው ” አሉ ዮናታን ።
ለዚህማ ምን ምክር ያስፈልገዋል ? ” አለ እስክንድር“ “ እሱ ራሱ ለመተው በቋፍ ነው ያለው ። ”
“ የለም እሱ የራሱን ውሳኔ ወስዶ ከተወማ አሁን ባለበት ሁኔታ ለእኔዴም ለሁሌም ነው የሚተወው
ጭራሽ ወደ ትምህርት ፊቱን አይመልስም ምክሩ የሚያስፈልገው ጤናማ በሆነ አመለካከት ትምህርቱን አቋርጦ አእምሮው ሲረጋጋ እንዲመለስበት ነው” አሉና ዮናታን አንድ ሐሳብ ድንገት ስለ መጣባቸው፡ “ ደግሞ አይምሰልህ
ለማቋረጥ ድፍረት የሚኖረው አይምሰልህ ማለቴ ትምህርቱን ለመተው ድፍረት ባያጣም ዩኒቨርስቲውን መልቀቅ
ድፍረት አይኖረውም አሉ።
«« አልገባኝም ” አለ እስክንድር ግር ብሎት
በዐይኑ ያፈቀራት ልጅ ያለችወታ እዚሁ ግቢ ነው አላልከኝም ? ”
“ አዎ ፥ መቼም በግምቴ ይመስለኛል ”
“ታዲያ እሷ ያለችበትን ግቢ እንዴት ችሎ ይልቃል!”
“ እ? ”
« እንዳው ስታስበው ችሎ እሚለቅ ይመስልሃል ወይ ?”
"እህ...
“ ራስ ግሪል ” የምትል ዓርማ ከደረቱ ላይ የለጠፈች አስተናጋጅ ፡ “ ምን ልታዘዝ ?” ሲል ከፊቱ መጥቶ ቆመ ።
እስቲ ቀዝቃዛ ቢራ ” አለ ለማ ሰዓቱን እየተመለከተ
ዘጠኝ ከዐሥር ሆኖ ነበር ። “ ቦታው ጠፍቷት ይሆን እንዴ ?” ሲል አሰበ ፥ ምናልባት ዋናው ራስ ሆቴል ሔዳ እንደሆን በሚል ግምት ። ነገር ግን ቀጠሮአቸውን በደንብ ያስታውሳል ። “ራስ ግሪል ፡ ቅዳሜ በዘጠኝ ሰዓት” ሲላት
ጥቂትም ግር ሳይላት ነበር ቀጠሮውን የተቀበለችው ።
“ እንዴት አባቷ ቀጠሮው ቦታ ቀድማ አትገኝም ? የሚል ትምክህት ተሰማው ። ለጊዜው ተፈላጊ በመሆኑ ዐሥር ደቂቃ አሳልፎ የመጣው ቀድማ ትጠብቀኛለች በሚል ግምት ነበር ።
አሳላፊው ቢራውን ይዞለት መጣ ።
ለማ የቢራውን ቅዝቃዜ ለመገመት ጠርሙሱን በእጁ ጠበቅ አርጎ ከጨበጠ በኋላ አስከፈተ ። ሁለቴ ተጐንጭቶ
ግማሽ ወገቡ ላይ አደረሰው ።የዕለቱ ወበቅ ሌላ ጉዳይ ነበር ።ኮቱን አወለቀ ፡ ከፊት ለፊቱ በከረባት ታንቀው የተቀመ
ጡትን ወፍራም ሰውዬ ተመልክቶ ፡ ሙቀት በመቋቋም ችሎታቸው ተደነቀ ።
ደቂቃዎቹ ወደፊት ተራመዱ ። ወፈር ያለች አጭር ልጅ ግን ብቅም ኣላለች ። አምስት ደቂቃ ሳይሆን ሙሉ ቀን የጠበቃትን ያህል ስሜቱ ተቁነጠነጠ ። ከአሁን በፊት ሁለት ጊዜ ሴቶች በቀጠሮ ቀጥተውታል ብዙ ሴቶች በመጀመሪያ ቀጠሮ ላይ እንዲህ እንደሚያረጉ ያውቃል ።ርካሽ እንዳይምስሉ የሚያደርጉት መፍጨርጨር ነው ። ይሁን እንጂ
በቤተ ልሔም ሊቀጣ አይፈልግም መቅረት ሳይሆን መዘግየቷ ራሱ ምን ሲደረግ !
ቢራውን ጭልጥ አድርጎ ተነሥቶ ሊሔድ ፈለገ ። ነገር ግን እግሩን አሳነቃነቀም ። ነገር የጠፋው የዚያች የሰርግ ዕለት ነው "አፌኝ ካጠፋሁ አይቀር ፥ ማስጨረስ አለብኝ? የሚል ስሜት አደረበት ።የቤተ ልሔም ግምት ልክ ነበር ።የተዘበራረቀ ስሜቱን ተመርኩዞ መከረኛ ኅሊናው የፌዝ
ጥርሱን እያሳየ ከተፍ አለበት ። እንደ ገና ሁለት ለማዎች ሙግት ጀመሩ ።
ምነው ቢቀርብህ ለማ?”
• ምኑ ?
• ዝቀጡ " ያለቦታህ መዋሉ !”
• መምህር የሚያሰተምራትን ኮረዳ ሲያወጣ መዝቀጥ አይደለም ። ማነው እንዲህ ያለው? ማነው እንዲህ አይነት
ሕግ የደነገገው ? አላየሁም አላነበብኩም እስካሁን ጅል ሆኜ ቆይቻለሁ ቁጥብነቴ በሕይወቴ ላይ ምን ጨመረልኝ? ፍራፍሬ ቀርቦ አትብሉ ብሎ የሚያግድ ሕግ ካለ አልቀበልም።
መታገድ ሳይሆን መቆጠብ ያስፈልጋል ።
መቆጠብ መቆጠብያ ከአመጋግብ መቆጠብ ከቃልባዊ ግንኙነት መቆጠብ ቁጥብነትን የሰውነት መለኪያ ያደረገው ማነው ? ”
“ አመዛዛኝ እንጂ ቁጥብነት ከኔ ለማ ሰልማ የሰው ልጅ ሕይወት ከእንስሶች ባልተለየ ነበር ። እንደ እንስሶች በተገናኙበት መዳራት ፡ ባገኙበት መብላት መጠጣት : በደረሱበት ወቅ
ኛት ፡ ያገኙትን ማንሣት ፡ የጠሉትን መጥላት ቢሆንማ ፥ታላቅ የስሜት ግጭት ስለሚፈጠር የሰው ልጅ እርስ በርሱ ይተላለቅ ነበር ። ቁጥብነት በስሜት ሳይጋጩ ተባብሮ መኖ
ርን በሚፈልግ ኅብረተሰብ ውስጥ ያለ ማኅበራዊ ሕግ ነው . .
እና የአካባቢውን ሕግ ብጥስ ምን ይመጣብኛል ??
መተፋት ነዋ ! በኅብረተሰብ መታፋት መናቅ
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
...ማለቴ በአሁኑ ጊዜ እንኳ ሳምንት ወደኋል የቀረባችውን የትምህርት ዐይነቶች ለማሟላት ብዙ መጽሐፍ ያገላብጣል ብዬ ቃል መግባቱ ያስፈራኛል ” አላቸው ።
ዮናታን ነገሩ ስለገባቸው ደብዛዛ ፈገግታ አሳዩ ። ግን ብዙም ሳይቆዩ ፈገግታው ጭልም ብሎ ጠፍቶ ፊታቸው ተለዋወጠ ግንባራቸው ላይ ትልቅ የደምሥር ተምዘግዝጎ ወጣ ፤ ቅጽበታዊ ውሳኔ ከአእምሮአቸው ታዞ ምላሳቸውጋ
ደርሶ ነበር ።
ቃላቱን ከመወርወራቸው በፊት ያለምክንያት መነጽ ራቸውን አወለቁ ። እንደ ወትሮአቸው ዐይናቸውን ሳያሹ
መልሰው አደረጉት ። ወደ ኋላቸው ተለጥጠው ተቀመጡ ።እናም ተነፈሱ ።
ይህን ዓመት ትምህርቱን ማቋረጥ ይኖርበታል በኔ ግምት ።
እስክንድር ግር አለው፤ዝም ብሎ እያያቸው “ እና በምን ዐይነት መንገድ ልንመክረው እንችላለን ? አለ በልቡ ።
“ ምን ዐይነትምክር ነው ትምህርትን አቋርጥ ብሎ ምክር?”
“እህሳ ምነው ዝም አልክ?” አሉት ።
ትንሽ ሲያመነታ ቆየና ። “ ግን ይህችን ዓመት እንደ ምንም ጨርሶ ቢገላገል አይሻልም ? ” አላቸው ።
“ ትምህርት የሚገላገሉት ዕዳ ነው እንዴ ? ”
ማለቴ ” አለ እስክንድር ሐሳባቸው ስለ ገባው ቶሎ ብሎ በማደናገር ዐይነት ። “ ሌላ ዓመት መጨመሩ ራሱ የበለጠ ሊረብሽው ይችላል ብዬ ነው፤ ጓደኞቹ ሥራ ይዘው ሲያይ ይሄ ጊዜያዊ ሁኔታ ነው ጊዜያዊ ችግር ነው ። እኔ የማስበው ግን ከዘላቂ ሕይወቱ አንጻር ነው ። በእኔ ግምት አቤል ከጤናማ አእምሮው ጋር መመረቅ አለበት ። ከዚያ በኋላ ሥራ ይዞ ገንዘብ ማግኘት ሳይሆን ለዓለም አንድ ነገር ማበርከት ይሆናል ሕልሙ ” አሉና ዮናታን ከመጽሐፍ መደርደሪያቸው ላይ እንድ ጥራዝ አንሥተው አቤል በድጋሚ ሠርቶ የሰጣቸው የጥናት ጽሑፍ ነበር
«« ይኸውልህ ” አሉት። የጽሑፉን መግቢያ ዐልፈው መሐል ገጾቹን እያሳዩትጨ “ ከዚህ እስከዚህ ያለው ጽሑፍ የተቀዳው “ አንቲ ዱሪንግ” ከሚለው የኤንግልስ መጽሐፍ ውስጥ ነው ። ሐሳቡን ማለቴ እንዳይመስልህ! ፤ አረፍተ ነገሩ ቀርቶ ቃላቱን እንኳ አልቀየረውም ፡ ከመሰላቸትም አልፎ ትምህርቱን የመጥላት ምልክት ነው አቤል እንዲህ ዐይነት ተማሪ አልነበረም እንዳለች ከመጽሐፍ ቀድቶ ማምጣት ቀርቶ ታላላቅ ምሁራን በደረሱዋቸው ታላላቅ ሥራዎች ላይ የሚያቀርበውን ሐሳብ ለመፍታት እንኳ ያስቸግር ነበር ። አምና በአንዲት ዲያሎግ ሽንጡን ገትሮ ይዞን አስራ አምስት ቀን ሙሉ እንዳንጫጫን ትዝ፤ አይልህም ? !እኔ ያኔ እሱ ባነሣት ጥያቄ የራሱን ምሁራዊ ብቁነት ተጠራጥሬ እንደገና መጻሕፍት ሳገላብጥ የከረምኩብት ጊዜ ነበር ።
አሁን ግን የዚያን ጊዜው አቤል አይደለም ችሎታው አለው ። ግን አንዳች ችግር ደርሶበታል ። ስለዚህ ችግሩ ከተገለጠ በኋላ ነው ትምህርቱን በሚገባ ሊያጠናቅቅ የሚችለው እንጂ አድበስብሰው ቢያሳልፉት ምንም ጥቅም
የለውም።
እስክንድር የጥናት ጽሑፉን ወረቀት እያየ ፈዞ ቀረ ።እንዳለ የመፀፉ ግልባጭ ነበር አቤል ይህን የጥናት አርስት ወስዶ እንደገና እንዲሰራ ዮናታን በመከሩት ጊዜ መልሶ ወስዶ ሲያምጥበት ዐሥራ አምስት ቀን ያህል አስቀመጠው ። በመጨረሻም ከጠቀሱት መጽሐፍ ውስጥ እንዳለ ገልብጦ ሰጣቸው አያውቁም ብሎ አልነበረም ይህን ያረገው ከእጁ እንዲወጣለት ብቻ እንጂ ።
“ እና አሁን ትምህርቱን እርም ብሎ ከመተዉ በፊት እንዲያቋርጥ በዘዴ ብንመክረው ” አሉ ዮናታን ።
ለዚህማ ምን ምክር ያስፈልገዋል ? ” አለ እስክንድር“ “ እሱ ራሱ ለመተው በቋፍ ነው ያለው ። ”
“ የለም እሱ የራሱን ውሳኔ ወስዶ ከተወማ አሁን ባለበት ሁኔታ ለእኔዴም ለሁሌም ነው የሚተወው
ጭራሽ ወደ ትምህርት ፊቱን አይመልስም ምክሩ የሚያስፈልገው ጤናማ በሆነ አመለካከት ትምህርቱን አቋርጦ አእምሮው ሲረጋጋ እንዲመለስበት ነው” አሉና ዮናታን አንድ ሐሳብ ድንገት ስለ መጣባቸው፡ “ ደግሞ አይምሰልህ
ለማቋረጥ ድፍረት የሚኖረው አይምሰልህ ማለቴ ትምህርቱን ለመተው ድፍረት ባያጣም ዩኒቨርስቲውን መልቀቅ
ድፍረት አይኖረውም አሉ።
«« አልገባኝም ” አለ እስክንድር ግር ብሎት
በዐይኑ ያፈቀራት ልጅ ያለችወታ እዚሁ ግቢ ነው አላልከኝም ? ”
“ አዎ ፥ መቼም በግምቴ ይመስለኛል ”
“ታዲያ እሷ ያለችበትን ግቢ እንዴት ችሎ ይልቃል!”
“ እ? ”
« እንዳው ስታስበው ችሎ እሚለቅ ይመስልሃል ወይ ?”
"እህ...
“ ራስ ግሪል ” የምትል ዓርማ ከደረቱ ላይ የለጠፈች አስተናጋጅ ፡ “ ምን ልታዘዝ ?” ሲል ከፊቱ መጥቶ ቆመ ።
እስቲ ቀዝቃዛ ቢራ ” አለ ለማ ሰዓቱን እየተመለከተ
ዘጠኝ ከዐሥር ሆኖ ነበር ። “ ቦታው ጠፍቷት ይሆን እንዴ ?” ሲል አሰበ ፥ ምናልባት ዋናው ራስ ሆቴል ሔዳ እንደሆን በሚል ግምት ። ነገር ግን ቀጠሮአቸውን በደንብ ያስታውሳል ። “ራስ ግሪል ፡ ቅዳሜ በዘጠኝ ሰዓት” ሲላት
ጥቂትም ግር ሳይላት ነበር ቀጠሮውን የተቀበለችው ።
“ እንዴት አባቷ ቀጠሮው ቦታ ቀድማ አትገኝም ? የሚል ትምክህት ተሰማው ። ለጊዜው ተፈላጊ በመሆኑ ዐሥር ደቂቃ አሳልፎ የመጣው ቀድማ ትጠብቀኛለች በሚል ግምት ነበር ።
አሳላፊው ቢራውን ይዞለት መጣ ።
ለማ የቢራውን ቅዝቃዜ ለመገመት ጠርሙሱን በእጁ ጠበቅ አርጎ ከጨበጠ በኋላ አስከፈተ ። ሁለቴ ተጐንጭቶ
ግማሽ ወገቡ ላይ አደረሰው ።የዕለቱ ወበቅ ሌላ ጉዳይ ነበር ።ኮቱን አወለቀ ፡ ከፊት ለፊቱ በከረባት ታንቀው የተቀመ
ጡትን ወፍራም ሰውዬ ተመልክቶ ፡ ሙቀት በመቋቋም ችሎታቸው ተደነቀ ።
ደቂቃዎቹ ወደፊት ተራመዱ ። ወፈር ያለች አጭር ልጅ ግን ብቅም ኣላለች ። አምስት ደቂቃ ሳይሆን ሙሉ ቀን የጠበቃትን ያህል ስሜቱ ተቁነጠነጠ ። ከአሁን በፊት ሁለት ጊዜ ሴቶች በቀጠሮ ቀጥተውታል ብዙ ሴቶች በመጀመሪያ ቀጠሮ ላይ እንዲህ እንደሚያረጉ ያውቃል ።ርካሽ እንዳይምስሉ የሚያደርጉት መፍጨርጨር ነው ። ይሁን እንጂ
በቤተ ልሔም ሊቀጣ አይፈልግም መቅረት ሳይሆን መዘግየቷ ራሱ ምን ሲደረግ !
ቢራውን ጭልጥ አድርጎ ተነሥቶ ሊሔድ ፈለገ ። ነገር ግን እግሩን አሳነቃነቀም ። ነገር የጠፋው የዚያች የሰርግ ዕለት ነው "አፌኝ ካጠፋሁ አይቀር ፥ ማስጨረስ አለብኝ? የሚል ስሜት አደረበት ።የቤተ ልሔም ግምት ልክ ነበር ።የተዘበራረቀ ስሜቱን ተመርኩዞ መከረኛ ኅሊናው የፌዝ
ጥርሱን እያሳየ ከተፍ አለበት ። እንደ ገና ሁለት ለማዎች ሙግት ጀመሩ ።
ምነው ቢቀርብህ ለማ?”
• ምኑ ?
• ዝቀጡ " ያለቦታህ መዋሉ !”
• መምህር የሚያሰተምራትን ኮረዳ ሲያወጣ መዝቀጥ አይደለም ። ማነው እንዲህ ያለው? ማነው እንዲህ አይነት
ሕግ የደነገገው ? አላየሁም አላነበብኩም እስካሁን ጅል ሆኜ ቆይቻለሁ ቁጥብነቴ በሕይወቴ ላይ ምን ጨመረልኝ? ፍራፍሬ ቀርቦ አትብሉ ብሎ የሚያግድ ሕግ ካለ አልቀበልም።
መታገድ ሳይሆን መቆጠብ ያስፈልጋል ።
መቆጠብ መቆጠብያ ከአመጋግብ መቆጠብ ከቃልባዊ ግንኙነት መቆጠብ ቁጥብነትን የሰውነት መለኪያ ያደረገው ማነው ? ”
“ አመዛዛኝ እንጂ ቁጥብነት ከኔ ለማ ሰልማ የሰው ልጅ ሕይወት ከእንስሶች ባልተለየ ነበር ። እንደ እንስሶች በተገናኙበት መዳራት ፡ ባገኙበት መብላት መጠጣት : በደረሱበት ወቅ
ኛት ፡ ያገኙትን ማንሣት ፡ የጠሉትን መጥላት ቢሆንማ ፥ታላቅ የስሜት ግጭት ስለሚፈጠር የሰው ልጅ እርስ በርሱ ይተላለቅ ነበር ። ቁጥብነት በስሜት ሳይጋጩ ተባብሮ መኖ
ርን በሚፈልግ ኅብረተሰብ ውስጥ ያለ ማኅበራዊ ሕግ ነው . .
እና የአካባቢውን ሕግ ብጥስ ምን ይመጣብኛል ??
መተፋት ነዋ ! በኅብረተሰብ መታፋት መናቅ
👍1
ከአውሬ ወይም ከእንስሳ መቆጠር ! መዝቀጥ?
ለማ ድንጋት ዘመር ቢል ፊቱን ከህንፃው ጋር ከተሰራው ረዥም የቁም መሰታወት ውስጥ ቀ ተመለከተ " በውን ከጠላቱ ጋር እንደሚሟገት ሰው ግንባሩ ተኮማትሮ "ፊቱ የውስጥ ስሜቱን በግልፅ ያሳይ ነበር።
ከኅሊና የበለጠ ጠላት ምን እለ?
« አዎ ! ጠላትህ ነኝ ከሰውነት ወጭ ስትሆን ገና የባሰ ጠላትህ እሆናለሁ ። ሕይወትህ የአንዱ መሆን አለበት !
የውጭያዊ አንነትህ ወይም የውስጣዊ እንተነትህ!
“ ኦፍ ! በቃኝ ሙግት አልፈልግም ? ?
“ እንዴት ? ”
• እንዲህ ነዋ ! ትዳር መመሥረት አልቻልኩም ። ምን ተይዞ ጉዞ ! ”
“ እና የአሁኑ ተግባርህ ለዚህ ሁሉ መካካሻ ነው ? !
“ ከረሜላ ካልተገዛልኝ ብርጭቆ እሰብራለሁ ” እንደሚል ሕፃን ወይም ደግሞ ፥ “ የሲኒማ ፍራንክ ካልሰጠሽኝ እናቴ አይደለሽም ! ”? ብሎ ደሀ እናቱን እንደሚያስፈራራ ጎረምሳ ሆንክ ኳ ! ነው ፡ አይደለም ? አልቤርጎ እየኖሩ ክብር
የለም ።
ምንም ሆነ ምን በቁጥብነት ራሴን አላስርም ፡ ካለመቆጠቤ የሚቀርብኝ ክብሬ...
' ለማኅበራዊ ችግር መፍትሔው : ማኅበራዊ ትግል እንጂ ካሉበት በታች ሆኖ መገኘት እይደለም!”
ኦፍ !
በቀይ እጅጌ ጉርድ ቀሚስ ደምቃ ጽጌረዳ አበባ የመሰለች ኮረዳ ወደ ምግብ ቤቱ ስትገባ በተመለከተ ጊዜ
ሲወተውተው የቆየው ኅሊናው የኋሊት ፈረጠጠለት ።
ጎሽ ፡ ገላገልሽኝ” በማለት ዐይነት ለማ በረዥሙ ተንፍሶ ተመቻችቶ ተቀመጠ ። ነገር ግን የውስጥ ስሜቱን በፈገግታ
ሊገልጽ አልፈለገም ። ቅሬታውን በሚያንጸባርቅ አስተያየት
ተቀበላት።
“ሶሪ ፤ ብዙ እስጠበቅሁህ አይደል? ” አለችው ቤተልሔም ፡ ቁና ቁና እየተነፈሰች ። “ ኦፍ አገኝሃለሁ የሚል ግምት አልነበረኝም ተስፋ ቆርጨ ነበር
እንዳለችውም ገና በሩን ስትገባ ዐይኖቿ ከወንዶቹ መሐል አነጣጥረው ለማን ባገኙት ጊዜ፥ ልቧ በደስታ ከውስጧ ዘሎ ሊወጣ ምንም አልቀረው ። በመዘግየቷ ጥፋተኝነት እየተሰማት ነበር የቀረበችው ለማ መቆጣት አልቻለም ።መላ ሰውነቷን የተርከፈከፈችው ሽቶ መዓዛ ስሜቱን አደንዝዞት ፡ ቅሬታወን እንዲውጥ አስገደደው ።
ምንም አይደለም ፥ በይ ቁጭ በይ ። ግን ምነው ? ”አላት ፥ ግንባሩን አላልቶ ሰዓቱን እያየ ። ዘጠኝ ተኩል ሆኖ ነበር ።
“ አንድ ደረቅ ባለታክሲ አጋጥሞኝ” ኮ ነው” አለች ቤተልሔም ከአቀማመጧ እየተመቻቸች ። “ እኛን ውስጥ አጉሮ ነዳጅ ለመቅዳት አይገተር መሰለህ ? ”
“ጥላችሁት በሌሳ ታክሲ አትሔዱም ነበር? ! ” አላት ! በመቆርቆር ስሜት ።
“ መጥፎ አካባቢ ነበራ ! ታክሲ እንደ ልብ የማይገኝበት
አንድ አሳላፊ መጥቶ ከፊታቸው ቆመ ።
“ የብርቱካን ጭማቂ አለ ? ” ስትል ጠየቀች ።
ምነው ? ቢራ ጠጭ እንጂ ” አላት ለማ ።
አልጠጣም ። በዚህ በፀሐይ በቢራ ራሴን ይፈልጠዋል ” አለችውና ፊቷን ወደ አሳላፊው መልሳ' “ ጭማቂውን አምጣልኝ ” ስትል አዘዘች ።
በል ለእኔም ቢራ ድግመኝ ” አለ ለማ ።
ፀሐዩን ፈርታ ሳይሆን ቢራ እጅግም ነች ። ቦርጭ ያወጣል እያሉ ጓደኞቿ ስለሚያስፈራሯት ትታዋለች ።ሌላው ችግሯ ደግሞ ቢራ ከጠጣች ሽንት ቤቱ ለእሷ ብቻ መለቀቅ አለበት ። በጉሮሮዋ ከመውረዱ ሽንቷ ይመጣባታል ። ውስኪ ሲሆን ነው ደስ ብሎአት የምትጠጣው ።
“ውይ ! ምን ዐይነት ቃጠሎ ቀን ነው?” ስትል ጨዋታ ከፈተች ። ስስ ተካፋች ሹራቧን አውልቃ ትከሻና ደረትዋን ገላልጣ ነበር የተቀመጠችው የቆዳዋ ጥራት በሞግዚት ተንከባክበው የያዙት እንጂ በዩኒቨርስቲ ትምህርት የማቀቀ
አይመስልም ።
“ ጉድ ነው እንጂ” አለና ለማ ወበቁን በማጋነን አይነት ወዲያው መለስ አርጎ ' “ እኔስ ቦታውን ወይም ቀጠሮውን ረስተሽዋል ብዬ ነበር” አላት ።
አሳላፊው ቢራውንና ጭማቂውን አቅርቦላቸው ተመለሰ።
“ እንዴ! ምን ማለትህ ነው?” አለችው ፡ ልቡ ውስጥ ገብታ ለመጐዝጐዝ ዐይኗን እያስለመለመች ። “ እንዴት
እረሳዋለሁ ?! ””
እውነትም ቤተልሔም አትረሳም ። ከዚህ ቀደም የሶስት ቦይፍሬንዶቿን ቀጠሮ እያወጣች እያወረደች ስታማርጥ
ውላ የአንድ ትልቅ መሥሪያ ቤት ኃላፊ ወደ ሆነው ዘንድ ወስና ብትሔድ ፡ ግማሽ ሰዓት በመዘግየቷ ና ወፍራም ገቢ
ያስገኝልኛል ብላ የተማመነችበትን የክረምት ሥራ ሳታገኝ ቀርታለች ።
ከዚያን ዕለት ወዲህ ቤተልሔም ቀጠሮ አትረሳም እንዳውም ጥቅም ያለበት ዐይነት ከሆነ ዝግጅቷን የምትጀም
ረው ገና በዋዜማው ነው ። ልብሷንና የሽቶዋን ዐይነት ስትመራርጥ ታመሻለች አነጋገሯን ፡ ቅልጥፍናዋን ስታስብበት ታድራለች ። ባዶ የፍቅር ዜማ እያንጐራጐረ የሚጠብቃትን ወንድ አውቶቡስ ፌርማታ ጥግ ገትራ ሲኒማ ቤት የምትዝናናውን ያህል መልካም ዝና ወይም ገንዘብ ያለውን ላለማስጠበቅ በጥድፊያ ሁለት ታክሲ የምታስቆምበት ጊዜ አለ ፡ ያም ሆነ ይህ ያን “ ለታ አልያዘላትም ። ስለዚህ እማይደገም ዕድል አመለጣት ። ሰውዬውን በሌላ ቀን አገኘው ይሆናል ብላ ብታስብም ከአዲስ አበባ መንገዶች አጣችው "
ቤተልሔም ከቀጠሮ ይበልጥ የማትረሳው ሌላው ነግር የዛሬ ዓመት“ፍሬሽ ማን” ሆና የደረሰባት ነው። ፈገግታ እማይላየው አንድ ወጣት የኢኮኖሚክስ ሌክቸረር ነበር ታዲያ ትምህርቱ እየከበዳት ሒደና በሱ ኃይል ለማለፍ ፈለገች ።
💥ይቀጥላል💥
ለማ ድንጋት ዘመር ቢል ፊቱን ከህንፃው ጋር ከተሰራው ረዥም የቁም መሰታወት ውስጥ ቀ ተመለከተ " በውን ከጠላቱ ጋር እንደሚሟገት ሰው ግንባሩ ተኮማትሮ "ፊቱ የውስጥ ስሜቱን በግልፅ ያሳይ ነበር።
ከኅሊና የበለጠ ጠላት ምን እለ?
« አዎ ! ጠላትህ ነኝ ከሰውነት ወጭ ስትሆን ገና የባሰ ጠላትህ እሆናለሁ ። ሕይወትህ የአንዱ መሆን አለበት !
የውጭያዊ አንነትህ ወይም የውስጣዊ እንተነትህ!
“ ኦፍ ! በቃኝ ሙግት አልፈልግም ? ?
“ እንዴት ? ”
• እንዲህ ነዋ ! ትዳር መመሥረት አልቻልኩም ። ምን ተይዞ ጉዞ ! ”
“ እና የአሁኑ ተግባርህ ለዚህ ሁሉ መካካሻ ነው ? !
“ ከረሜላ ካልተገዛልኝ ብርጭቆ እሰብራለሁ ” እንደሚል ሕፃን ወይም ደግሞ ፥ “ የሲኒማ ፍራንክ ካልሰጠሽኝ እናቴ አይደለሽም ! ”? ብሎ ደሀ እናቱን እንደሚያስፈራራ ጎረምሳ ሆንክ ኳ ! ነው ፡ አይደለም ? አልቤርጎ እየኖሩ ክብር
የለም ።
ምንም ሆነ ምን በቁጥብነት ራሴን አላስርም ፡ ካለመቆጠቤ የሚቀርብኝ ክብሬ...
' ለማኅበራዊ ችግር መፍትሔው : ማኅበራዊ ትግል እንጂ ካሉበት በታች ሆኖ መገኘት እይደለም!”
ኦፍ !
በቀይ እጅጌ ጉርድ ቀሚስ ደምቃ ጽጌረዳ አበባ የመሰለች ኮረዳ ወደ ምግብ ቤቱ ስትገባ በተመለከተ ጊዜ
ሲወተውተው የቆየው ኅሊናው የኋሊት ፈረጠጠለት ።
ጎሽ ፡ ገላገልሽኝ” በማለት ዐይነት ለማ በረዥሙ ተንፍሶ ተመቻችቶ ተቀመጠ ። ነገር ግን የውስጥ ስሜቱን በፈገግታ
ሊገልጽ አልፈለገም ። ቅሬታውን በሚያንጸባርቅ አስተያየት
ተቀበላት።
“ሶሪ ፤ ብዙ እስጠበቅሁህ አይደል? ” አለችው ቤተልሔም ፡ ቁና ቁና እየተነፈሰች ። “ ኦፍ አገኝሃለሁ የሚል ግምት አልነበረኝም ተስፋ ቆርጨ ነበር
እንዳለችውም ገና በሩን ስትገባ ዐይኖቿ ከወንዶቹ መሐል አነጣጥረው ለማን ባገኙት ጊዜ፥ ልቧ በደስታ ከውስጧ ዘሎ ሊወጣ ምንም አልቀረው ። በመዘግየቷ ጥፋተኝነት እየተሰማት ነበር የቀረበችው ለማ መቆጣት አልቻለም ።መላ ሰውነቷን የተርከፈከፈችው ሽቶ መዓዛ ስሜቱን አደንዝዞት ፡ ቅሬታወን እንዲውጥ አስገደደው ።
ምንም አይደለም ፥ በይ ቁጭ በይ ። ግን ምነው ? ”አላት ፥ ግንባሩን አላልቶ ሰዓቱን እያየ ። ዘጠኝ ተኩል ሆኖ ነበር ።
“ አንድ ደረቅ ባለታክሲ አጋጥሞኝ” ኮ ነው” አለች ቤተልሔም ከአቀማመጧ እየተመቻቸች ። “ እኛን ውስጥ አጉሮ ነዳጅ ለመቅዳት አይገተር መሰለህ ? ”
“ጥላችሁት በሌሳ ታክሲ አትሔዱም ነበር? ! ” አላት ! በመቆርቆር ስሜት ።
“ መጥፎ አካባቢ ነበራ ! ታክሲ እንደ ልብ የማይገኝበት
አንድ አሳላፊ መጥቶ ከፊታቸው ቆመ ።
“ የብርቱካን ጭማቂ አለ ? ” ስትል ጠየቀች ።
ምነው ? ቢራ ጠጭ እንጂ ” አላት ለማ ።
አልጠጣም ። በዚህ በፀሐይ በቢራ ራሴን ይፈልጠዋል ” አለችውና ፊቷን ወደ አሳላፊው መልሳ' “ ጭማቂውን አምጣልኝ ” ስትል አዘዘች ።
በል ለእኔም ቢራ ድግመኝ ” አለ ለማ ።
ፀሐዩን ፈርታ ሳይሆን ቢራ እጅግም ነች ። ቦርጭ ያወጣል እያሉ ጓደኞቿ ስለሚያስፈራሯት ትታዋለች ።ሌላው ችግሯ ደግሞ ቢራ ከጠጣች ሽንት ቤቱ ለእሷ ብቻ መለቀቅ አለበት ። በጉሮሮዋ ከመውረዱ ሽንቷ ይመጣባታል ። ውስኪ ሲሆን ነው ደስ ብሎአት የምትጠጣው ።
“ውይ ! ምን ዐይነት ቃጠሎ ቀን ነው?” ስትል ጨዋታ ከፈተች ። ስስ ተካፋች ሹራቧን አውልቃ ትከሻና ደረትዋን ገላልጣ ነበር የተቀመጠችው የቆዳዋ ጥራት በሞግዚት ተንከባክበው የያዙት እንጂ በዩኒቨርስቲ ትምህርት የማቀቀ
አይመስልም ።
“ ጉድ ነው እንጂ” አለና ለማ ወበቁን በማጋነን አይነት ወዲያው መለስ አርጎ ' “ እኔስ ቦታውን ወይም ቀጠሮውን ረስተሽዋል ብዬ ነበር” አላት ።
አሳላፊው ቢራውንና ጭማቂውን አቅርቦላቸው ተመለሰ።
“ እንዴ! ምን ማለትህ ነው?” አለችው ፡ ልቡ ውስጥ ገብታ ለመጐዝጐዝ ዐይኗን እያስለመለመች ። “ እንዴት
እረሳዋለሁ ?! ””
እውነትም ቤተልሔም አትረሳም ። ከዚህ ቀደም የሶስት ቦይፍሬንዶቿን ቀጠሮ እያወጣች እያወረደች ስታማርጥ
ውላ የአንድ ትልቅ መሥሪያ ቤት ኃላፊ ወደ ሆነው ዘንድ ወስና ብትሔድ ፡ ግማሽ ሰዓት በመዘግየቷ ና ወፍራም ገቢ
ያስገኝልኛል ብላ የተማመነችበትን የክረምት ሥራ ሳታገኝ ቀርታለች ።
ከዚያን ዕለት ወዲህ ቤተልሔም ቀጠሮ አትረሳም እንዳውም ጥቅም ያለበት ዐይነት ከሆነ ዝግጅቷን የምትጀም
ረው ገና በዋዜማው ነው ። ልብሷንና የሽቶዋን ዐይነት ስትመራርጥ ታመሻለች አነጋገሯን ፡ ቅልጥፍናዋን ስታስብበት ታድራለች ። ባዶ የፍቅር ዜማ እያንጐራጐረ የሚጠብቃትን ወንድ አውቶቡስ ፌርማታ ጥግ ገትራ ሲኒማ ቤት የምትዝናናውን ያህል መልካም ዝና ወይም ገንዘብ ያለውን ላለማስጠበቅ በጥድፊያ ሁለት ታክሲ የምታስቆምበት ጊዜ አለ ፡ ያም ሆነ ይህ ያን “ ለታ አልያዘላትም ። ስለዚህ እማይደገም ዕድል አመለጣት ። ሰውዬውን በሌላ ቀን አገኘው ይሆናል ብላ ብታስብም ከአዲስ አበባ መንገዶች አጣችው "
ቤተልሔም ከቀጠሮ ይበልጥ የማትረሳው ሌላው ነግር የዛሬ ዓመት“ፍሬሽ ማን” ሆና የደረሰባት ነው። ፈገግታ እማይላየው አንድ ወጣት የኢኮኖሚክስ ሌክቸረር ነበር ታዲያ ትምህርቱ እየከበዳት ሒደና በሱ ኃይል ለማለፍ ፈለገች ።
💥ይቀጥላል💥
#የታካሚው_ማስታወሻ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
“ወደ ዚህ ስትመጣ የመጀመሪያህ ነው?”
“አዎ።”
“ትቆያለህ?”
ሳምንት አካባቢ።”
“እዚያ ማዶ ሚታየው አፄ ዮሐንስ አንገታቸው የተቀላበት ቦታ ነው።” እጁን ከመንገዱ በላይ እየጠቆመ::
“መተማ ዮሐንስ ደረስን ማለት ነው?”
“አዎ፡፡ አሁን ገብተናል፡፡” ልቤ ድንግጥ ድንግጥ አለብኝ፡፡ ሚኒባሱ እየቆመ፣ ሰዎችን ያወርዳል። እስከዛሬ ያልተሰማኝ ፍርሀት እየተሰማኝ ነው፡፡ ዝም አልኩ፡፡ ወደ ስንብት እየተጠጋሁ ነው፡፡
የማውራትም የማወቅም ፍላጎት የለኝም፡፡ ዝም ብዬ በዐይኔ ከተማውን መፈለግ ጀምረኩ፡፡ በግራና በቀኝ የተደረደሩ የጭቃ ቤቶች፣ ጭር ያለ ከተማ ነው፡፡ እንደጠበኩት ግርግር የበዛበት ከተማ አይደለም፡፡ ሰዐቴን አየሁ፤ አስር ተኩል፡፡ አብዛኛው ሰው ወርዶ አልቋል፡፡
“መናኸሪያ ትገባለህ?” ወያላው ፊቱን አዙሮ ጠየቀኝ፡፡
“አይ አልገባም፡፡”
“ካልገባህ መጨረሻው እዚህ ነው።”
“እሺ አውርደኝ!”
በጭራሽ እንደገመትኩት አይደለም፡፡ ለማደሪያ ሚሆን አልጋ ቤት እንኳን እስካሁን አላየሁም፡፡ ከተማዋ ትሞቃለች። አስራ አንድ ሰዓት እየሆነ ቢሆንም፣ በጣም ይወብቃል፡፡ ፍርሀት ነው መሰል፣ በጣም እያላበኝ ነው። ዝም ብዬ ዋና መንገዱን ይዤ፣ አልጋ ቤት ፍለጋ
ተጓዝኩኝ፡፡ ነጋዴ የሚርመሰመስበት፣ አዲስ ሰው፣ ፀጉረ ልውጥ ሰው
ከዐይን የማይገባበት ብዬ የገመትኩት ከተማ፣ ትንሽዬ መንደር ሆና አገኘኋት፡፡ መንገድ ዳር በብሎኬት የታጠረ ሰፊ ግቢ ያለው ሆቴል አየሁ፡፡ ሰላም ሆቴል ይላል፡፡ አላንገራገርኩም፡፡ ዘው ብዬ ገባሁ፡፡ ብቻ
አልጋ በኖረ፡፡
“አልጋ አለ?”
“አለ፡፡”
“እስቲ አሳዩኝ?”
“ባለሻወር ነው፣ ያለሻወር?”
“ባለሻወር፡፡” ቁልፍ አመጣችና አሳየችኝ፡፡
“ስንት ነው?”
“አንድ መቶ ሃምሳ ብር፡፡” ብሩን ሰጠኋትና ቦርሳዬን አስቀመጥኩ።
ሻወር ቤት ገብቼ ሻወር ቼክ ሳደርግ ውሀ የለችም፡፡ ዞር ስል፣ውሀ በባልዲ ተቀምጧል፡፡ በጣም አልቦኛል፣ ተለቃለኩኝ፡፡ እራት በልቼ ቢራ መጠጣት ጀመርኩ፡፡ ሙቀት ስለሆነ ተጠጣልኝ፡፡ ማታ ጥሩ እንቅልፍ ተኝቼ አደርኩ፡፡ ቀን ወጥቼ ከተማውን ዙሪያውን ሳይ ዋልኩ፡፡
በፍፁም እኔ እንዳሰብኩት አይደለም፡፡ የከተማው ዙሪያ ለጥ ያለ ለእርሻ የሚውል ሜዳ ሲሆን፣ ዛፎች በእርቀት ነው የሚገኙት፡፡ ስዞር ውዬ አመሻሹ ላይ፣ ቢራዬን እየጠጣሁ ምን እንደሚችል ሳስብ፣ አርሴማ ገዳም የሚል ሀሳብ መጣብኝ፡፡
#ኑሮ_በገዳም
ሽቅብ ዝግዛግ ሆኖ በተሰራውን የጥረጊያ መንገድረገ፣ በግራና በቀኝ በዛፎች ተከቧል፡፡ ከፊት ለፊቴ፣ አጠር ያለ ወጣት፣ የክርስቲያኖ ሮናልዶ ስዕል ያለበት ጥቁር የጨርቅ ሻንጣ በጀርባው ተሸክሞ በዝግታ ያዘግማል። እየተከታተልን ወደ ገዳሙ ዘልቀን ገባን። ከገዳሙ መግቢያ
በር ትንሽ ፈቅ ብላ ያለች የጭቃ ቤት ጋር ስንደርስ፤
“እንኳን ደህና መጣችሁ። ምዝገባ ቢጤ አለች።” አለን ፊቱ መጠጥ ያለ ጠይም ወጣት፡፡
“እሺ!” ብዬ ቆምኩኝ፡፡ ልጁን መዝግቦ ከጨርሰ በኋላ፣ ትንሽ ቆየኝ ብሎት እኔን መመዝግብ ጀመረ፡፡ ስም፣ እድሜ፣ የመጡበት አድራሻ፣ የአደጋ ግዜ ተጠሪ...፣ ሁሉንም ቀይሬ ነገርኩት፡፡
“ለስንት ግዜ ነው ሚቆዩት?”
“ለሦስት ሳምንት፡፡”
“መታወቂያ ይዘዋል?”
“አልያዝኩም፡፡” አልተጫነኝም፡፡
“እሺ፣ እንግዶቻችን፣ እኔ መልካሙ እባላለሁ፡፡ በገዳሙ አስተባባሪ ነኝ፡፡ አሁን ማደሪያ ቦታ እሰጣችኋለው፡፡ ገዳሙን
አስጎበኛችኋለው፤ ስለ ገዳሙ ታሪክ፣ መተዳደሪያ ደንብና ሌሎች መረጃዎችን እነግራችኋለው፡፡ እዚህ ገዳም፣ ማንኛውም አዲስ ሱባኤተኛ ሲገባ እናንተ እንዳደረጋችሁት ተመዝግቦ ነው፡፡ ገዳሙ የአርምሞ ገዳም ነው:: ማውራት ክልክል ነው፡፡ አስገዳጅ ነገር ካላጋጠማችሁ በስተቀር፣ ማውራት አይቻልም፡፡ የግድ ማውራት ካስፈለገ እንኳ፣ ዝግ ባለ ድምፅ፣ በለሆሳስ ነው ማውራት ሚቻለው፡፡ እዚህ መዳን የሚገኘው በአርምሞ ውስጥ ነው፡፡”
ከኛ ውጪ ለሌላ ሰው እንዳይሰማ፣ በሆዱ እንደሚያወራ፣ በጣም ዝግ ባለ ድምፅ ያወራናል፡፡ በአርምሞና በለሆሳስ ማለት እንዲህ ነው' ብዬ አሰብኩ፡፡ የሚያወራው እንዲሰማን፣ አንገታችንን ወደሱ አሰገግን፡፡ እያወራን ወደ ማደሪያችን ወሰደን፡፡ እያንዳንዱ ከሁለት መቶ ምዕመን በላይ የሚይዝ፣ አራት የማደሪያ አዳራሾች አሉ፡፡ ሁለቱ የወንድ፣ ሁለቱ የሴት እንደሆነ ነገረን፡፡ ቦታ ሊሰጠን ወደ አንደኛው አዳራሽ ይዞን ገባ፡፡ በውስጡ ከመቶ ሚበልጡ ምዕመናን አሉ፡፡አሰላሁት። በግምት በገዳሙ አንድ ሺህ የሚጠጉ ሱባኤያተኛ ምዕመናን
እንዳሉ ገመትኩኝ፡፡ ገዳሙ ግን ሰው ያለው አይመስልም፡፡ ዝም፣ ጭጭ፣ ያለ ነው፡፡ ሁሉም በለሆሳስ ፀሎት ላይ ነው፡፡ ሰላምታ እንኳ፣ ጎንበስ ቀና በመባባል ብቻ ነው፡፡ ምንም አይነት የሰው ድምፅ አይሰማም፡፡የወፎች ጭጭታና የዛፎች ሽው ሽውታ ብቻ ነው፡፡ በጣም ደስ ይላል፡፡መንፈስን ያድሳል፡፡ አዕምሮን ያረጋጋል፡፡ ፈውስ በመንፈስ ቅዱስ
ባይላክም እንኳ፣ የቦታው ድባብ ፈውስን ይሰጣል።
“እና ሌላው...” አለ መልካሙ ቦታችንን ሰጥቶን ከአዳራሹ ይዞን እየወጣ፣ “ማንኛውም ምእመን ወደ ገዳሙ ለሱባኤ ሲገባ፤ ፀጉሩን መላጨት፣ ንስሀ መግባትና ስግደት መውሰድ አለበት፡፡” አለን እኔን እኔን እየተመለከተ፡፡
“እሺ፡፡ ማን ነው ሚላጨን?”
“እርስ በእረስ ነው ምትለጫጩት፡፡ ፈራህ እንዴ..? አንተን እኔ ቆንጆ አድርጌ እላጭሃለው፡፡” የከተማ ልጅ መሆኔን አውቆ ነው መሰል፣ ከገባን ጀምሮ እኔን እኔን እየተመለከተ ነው ሲያወራ የነበረው፡፡
“እሺ” አልኩት፡፡ አሁን ስለራሴ ብዙም ግድ የለኝም፡፡ ምላጭ ግቢ ካለው ሱቅ ተገዝቶ ሁለታችንንም ላጨን፡፡ ነብስ ካወኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ፀጉሬን ተላጨሁ፡፡ እየላጨንም ስለ ገዳሙ መተዳደሪያ ደንብ ይነግረናል።
“በገዳሙ፣ በቀን ሁለት ጊዜ ብቻ ነው የሚበላው፡፡ ጥዋት ቅዳሴ እንዳለቀና ማታ አስራ ሁለት ሰዐት። አስራ ሁለት ሰዐት ካለፈ መመገብ አይቻልም፡፡ ገዳሙ መብራት ስለሌለው፣ ማታ ማታ ሻማ ነው
ምትጠቀሙት። ሻማ ከዚህ ሱቅ መግዛት ትችላላችሁ፡፡ የማታ ሦስት ሰዓት ፀሎት ካበቃ ቦሃላ ሻማ ማብራት አይቻልም፡፡ የእንቅልፍ ሰዓት ነው፡፡ እንዳያችሁት፣ የቦታ ጥበት ስላለ አንድ ሰው፣ በአንድ መዳበሪያ በታ ላይ ነው መተኛት ያለበት፡፡ የለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ፀሎት ላይ ሁሉም
ምዕመን መገኘት ግዴታ ነው፡፡” ሁለታችንንም ላጭቶ ሲጨርስ አስራ
አንድ ሰዐት ሆኖ የሰርክ ፕሮግራም ተጀመረ።
“በሉ ተነሱ እንሂድ፣ የሚቸግራችሁ ነገር ካለ እዚሁ ስላለን በፈለጋችሁት ሰዓት ጠይቁኝ ፤ ” ብሎ ፕሮግራሙ ወደ ሚካሄድበት ስፍራ ወሰደን፡፡
የገዳም ኑሮዬ ተጀመረ፡፡ ለሊት ዘጠኝ ሰዓት መነሳት በጣም ከባድ ነው፡፡ ግን፣ አማራጭ የለም፡፡ አስተባባሪዎች እየዞሩ ይቀሰቅሳሉ።ያልተነሳ ሰው ላይ ቀዝቃዛ ውሃ ይረጫሉ፡፡ የመጀመሪያ ቀናቶች ላይ
በጣም ከበደኝ፡፡ ከእንቅልፍ ሳልነቃ ውሃ ሲረጩኝ እንደ ኤሌክትሪክ ይነዝረኛል፡፡ ሁለት ሦስት ቀን ሲደጋግሙኝ፣ ገና ድምፃቸውን ስሰማ መነሳት ጀመርኩ፡፡ ፀሎትና ምህላው እስከ ጥዋቱ አስራ ሁለት ሰዓት ይደረጋል፤ ከዛ ወደ ፀበል።
ገዳሙን ቅጥር ግቢ በደንብ ለማማወቅ እየተዟዟርኩ ማየት ጀመርኩ፡፡ የአርሴማ ገዳም በሃገራችን እንዳሉት አብዛኞቹ ገዳማት፣በተራራማ ቦታ ላይ ከየተመሰረተ ነው፡፡ የገዳሙ መስራችና አስተዳዳሪ
የሆኑት መነኩሴ፣ እድሜያቸው ሃምሳ ዓመት ቢሆን ነው፡፡ ገዳሙ በእውቀት እንዲለማ በደንብ አስበውበት እንደመሰረቱት ገዳሙ አፍ አውጥቶ ይናገራል፡፡ ከመሰረቱት
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
“ወደ ዚህ ስትመጣ የመጀመሪያህ ነው?”
“አዎ።”
“ትቆያለህ?”
ሳምንት አካባቢ።”
“እዚያ ማዶ ሚታየው አፄ ዮሐንስ አንገታቸው የተቀላበት ቦታ ነው።” እጁን ከመንገዱ በላይ እየጠቆመ::
“መተማ ዮሐንስ ደረስን ማለት ነው?”
“አዎ፡፡ አሁን ገብተናል፡፡” ልቤ ድንግጥ ድንግጥ አለብኝ፡፡ ሚኒባሱ እየቆመ፣ ሰዎችን ያወርዳል። እስከዛሬ ያልተሰማኝ ፍርሀት እየተሰማኝ ነው፡፡ ዝም አልኩ፡፡ ወደ ስንብት እየተጠጋሁ ነው፡፡
የማውራትም የማወቅም ፍላጎት የለኝም፡፡ ዝም ብዬ በዐይኔ ከተማውን መፈለግ ጀምረኩ፡፡ በግራና በቀኝ የተደረደሩ የጭቃ ቤቶች፣ ጭር ያለ ከተማ ነው፡፡ እንደጠበኩት ግርግር የበዛበት ከተማ አይደለም፡፡ ሰዐቴን አየሁ፤ አስር ተኩል፡፡ አብዛኛው ሰው ወርዶ አልቋል፡፡
“መናኸሪያ ትገባለህ?” ወያላው ፊቱን አዙሮ ጠየቀኝ፡፡
“አይ አልገባም፡፡”
“ካልገባህ መጨረሻው እዚህ ነው።”
“እሺ አውርደኝ!”
በጭራሽ እንደገመትኩት አይደለም፡፡ ለማደሪያ ሚሆን አልጋ ቤት እንኳን እስካሁን አላየሁም፡፡ ከተማዋ ትሞቃለች። አስራ አንድ ሰዓት እየሆነ ቢሆንም፣ በጣም ይወብቃል፡፡ ፍርሀት ነው መሰል፣ በጣም እያላበኝ ነው። ዝም ብዬ ዋና መንገዱን ይዤ፣ አልጋ ቤት ፍለጋ
ተጓዝኩኝ፡፡ ነጋዴ የሚርመሰመስበት፣ አዲስ ሰው፣ ፀጉረ ልውጥ ሰው
ከዐይን የማይገባበት ብዬ የገመትኩት ከተማ፣ ትንሽዬ መንደር ሆና አገኘኋት፡፡ መንገድ ዳር በብሎኬት የታጠረ ሰፊ ግቢ ያለው ሆቴል አየሁ፡፡ ሰላም ሆቴል ይላል፡፡ አላንገራገርኩም፡፡ ዘው ብዬ ገባሁ፡፡ ብቻ
አልጋ በኖረ፡፡
“አልጋ አለ?”
“አለ፡፡”
“እስቲ አሳዩኝ?”
“ባለሻወር ነው፣ ያለሻወር?”
“ባለሻወር፡፡” ቁልፍ አመጣችና አሳየችኝ፡፡
“ስንት ነው?”
“አንድ መቶ ሃምሳ ብር፡፡” ብሩን ሰጠኋትና ቦርሳዬን አስቀመጥኩ።
ሻወር ቤት ገብቼ ሻወር ቼክ ሳደርግ ውሀ የለችም፡፡ ዞር ስል፣ውሀ በባልዲ ተቀምጧል፡፡ በጣም አልቦኛል፣ ተለቃለኩኝ፡፡ እራት በልቼ ቢራ መጠጣት ጀመርኩ፡፡ ሙቀት ስለሆነ ተጠጣልኝ፡፡ ማታ ጥሩ እንቅልፍ ተኝቼ አደርኩ፡፡ ቀን ወጥቼ ከተማውን ዙሪያውን ሳይ ዋልኩ፡፡
በፍፁም እኔ እንዳሰብኩት አይደለም፡፡ የከተማው ዙሪያ ለጥ ያለ ለእርሻ የሚውል ሜዳ ሲሆን፣ ዛፎች በእርቀት ነው የሚገኙት፡፡ ስዞር ውዬ አመሻሹ ላይ፣ ቢራዬን እየጠጣሁ ምን እንደሚችል ሳስብ፣ አርሴማ ገዳም የሚል ሀሳብ መጣብኝ፡፡
#ኑሮ_በገዳም
ሽቅብ ዝግዛግ ሆኖ በተሰራውን የጥረጊያ መንገድረገ፣ በግራና በቀኝ በዛፎች ተከቧል፡፡ ከፊት ለፊቴ፣ አጠር ያለ ወጣት፣ የክርስቲያኖ ሮናልዶ ስዕል ያለበት ጥቁር የጨርቅ ሻንጣ በጀርባው ተሸክሞ በዝግታ ያዘግማል። እየተከታተልን ወደ ገዳሙ ዘልቀን ገባን። ከገዳሙ መግቢያ
በር ትንሽ ፈቅ ብላ ያለች የጭቃ ቤት ጋር ስንደርስ፤
“እንኳን ደህና መጣችሁ። ምዝገባ ቢጤ አለች።” አለን ፊቱ መጠጥ ያለ ጠይም ወጣት፡፡
“እሺ!” ብዬ ቆምኩኝ፡፡ ልጁን መዝግቦ ከጨርሰ በኋላ፣ ትንሽ ቆየኝ ብሎት እኔን መመዝግብ ጀመረ፡፡ ስም፣ እድሜ፣ የመጡበት አድራሻ፣ የአደጋ ግዜ ተጠሪ...፣ ሁሉንም ቀይሬ ነገርኩት፡፡
“ለስንት ግዜ ነው ሚቆዩት?”
“ለሦስት ሳምንት፡፡”
“መታወቂያ ይዘዋል?”
“አልያዝኩም፡፡” አልተጫነኝም፡፡
“እሺ፣ እንግዶቻችን፣ እኔ መልካሙ እባላለሁ፡፡ በገዳሙ አስተባባሪ ነኝ፡፡ አሁን ማደሪያ ቦታ እሰጣችኋለው፡፡ ገዳሙን
አስጎበኛችኋለው፤ ስለ ገዳሙ ታሪክ፣ መተዳደሪያ ደንብና ሌሎች መረጃዎችን እነግራችኋለው፡፡ እዚህ ገዳም፣ ማንኛውም አዲስ ሱባኤተኛ ሲገባ እናንተ እንዳደረጋችሁት ተመዝግቦ ነው፡፡ ገዳሙ የአርምሞ ገዳም ነው:: ማውራት ክልክል ነው፡፡ አስገዳጅ ነገር ካላጋጠማችሁ በስተቀር፣ ማውራት አይቻልም፡፡ የግድ ማውራት ካስፈለገ እንኳ፣ ዝግ ባለ ድምፅ፣ በለሆሳስ ነው ማውራት ሚቻለው፡፡ እዚህ መዳን የሚገኘው በአርምሞ ውስጥ ነው፡፡”
ከኛ ውጪ ለሌላ ሰው እንዳይሰማ፣ በሆዱ እንደሚያወራ፣ በጣም ዝግ ባለ ድምፅ ያወራናል፡፡ በአርምሞና በለሆሳስ ማለት እንዲህ ነው' ብዬ አሰብኩ፡፡ የሚያወራው እንዲሰማን፣ አንገታችንን ወደሱ አሰገግን፡፡ እያወራን ወደ ማደሪያችን ወሰደን፡፡ እያንዳንዱ ከሁለት መቶ ምዕመን በላይ የሚይዝ፣ አራት የማደሪያ አዳራሾች አሉ፡፡ ሁለቱ የወንድ፣ ሁለቱ የሴት እንደሆነ ነገረን፡፡ ቦታ ሊሰጠን ወደ አንደኛው አዳራሽ ይዞን ገባ፡፡ በውስጡ ከመቶ ሚበልጡ ምዕመናን አሉ፡፡አሰላሁት። በግምት በገዳሙ አንድ ሺህ የሚጠጉ ሱባኤያተኛ ምዕመናን
እንዳሉ ገመትኩኝ፡፡ ገዳሙ ግን ሰው ያለው አይመስልም፡፡ ዝም፣ ጭጭ፣ ያለ ነው፡፡ ሁሉም በለሆሳስ ፀሎት ላይ ነው፡፡ ሰላምታ እንኳ፣ ጎንበስ ቀና በመባባል ብቻ ነው፡፡ ምንም አይነት የሰው ድምፅ አይሰማም፡፡የወፎች ጭጭታና የዛፎች ሽው ሽውታ ብቻ ነው፡፡ በጣም ደስ ይላል፡፡መንፈስን ያድሳል፡፡ አዕምሮን ያረጋጋል፡፡ ፈውስ በመንፈስ ቅዱስ
ባይላክም እንኳ፣ የቦታው ድባብ ፈውስን ይሰጣል።
“እና ሌላው...” አለ መልካሙ ቦታችንን ሰጥቶን ከአዳራሹ ይዞን እየወጣ፣ “ማንኛውም ምእመን ወደ ገዳሙ ለሱባኤ ሲገባ፤ ፀጉሩን መላጨት፣ ንስሀ መግባትና ስግደት መውሰድ አለበት፡፡” አለን እኔን እኔን እየተመለከተ፡፡
“እሺ፡፡ ማን ነው ሚላጨን?”
“እርስ በእረስ ነው ምትለጫጩት፡፡ ፈራህ እንዴ..? አንተን እኔ ቆንጆ አድርጌ እላጭሃለው፡፡” የከተማ ልጅ መሆኔን አውቆ ነው መሰል፣ ከገባን ጀምሮ እኔን እኔን እየተመለከተ ነው ሲያወራ የነበረው፡፡
“እሺ” አልኩት፡፡ አሁን ስለራሴ ብዙም ግድ የለኝም፡፡ ምላጭ ግቢ ካለው ሱቅ ተገዝቶ ሁለታችንንም ላጨን፡፡ ነብስ ካወኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ፀጉሬን ተላጨሁ፡፡ እየላጨንም ስለ ገዳሙ መተዳደሪያ ደንብ ይነግረናል።
“በገዳሙ፣ በቀን ሁለት ጊዜ ብቻ ነው የሚበላው፡፡ ጥዋት ቅዳሴ እንዳለቀና ማታ አስራ ሁለት ሰዐት። አስራ ሁለት ሰዐት ካለፈ መመገብ አይቻልም፡፡ ገዳሙ መብራት ስለሌለው፣ ማታ ማታ ሻማ ነው
ምትጠቀሙት። ሻማ ከዚህ ሱቅ መግዛት ትችላላችሁ፡፡ የማታ ሦስት ሰዓት ፀሎት ካበቃ ቦሃላ ሻማ ማብራት አይቻልም፡፡ የእንቅልፍ ሰዓት ነው፡፡ እንዳያችሁት፣ የቦታ ጥበት ስላለ አንድ ሰው፣ በአንድ መዳበሪያ በታ ላይ ነው መተኛት ያለበት፡፡ የለሊቱ ዘጠኝ ሰአት ፀሎት ላይ ሁሉም
ምዕመን መገኘት ግዴታ ነው፡፡” ሁለታችንንም ላጭቶ ሲጨርስ አስራ
አንድ ሰዐት ሆኖ የሰርክ ፕሮግራም ተጀመረ።
“በሉ ተነሱ እንሂድ፣ የሚቸግራችሁ ነገር ካለ እዚሁ ስላለን በፈለጋችሁት ሰዓት ጠይቁኝ ፤ ” ብሎ ፕሮግራሙ ወደ ሚካሄድበት ስፍራ ወሰደን፡፡
የገዳም ኑሮዬ ተጀመረ፡፡ ለሊት ዘጠኝ ሰዓት መነሳት በጣም ከባድ ነው፡፡ ግን፣ አማራጭ የለም፡፡ አስተባባሪዎች እየዞሩ ይቀሰቅሳሉ።ያልተነሳ ሰው ላይ ቀዝቃዛ ውሃ ይረጫሉ፡፡ የመጀመሪያ ቀናቶች ላይ
በጣም ከበደኝ፡፡ ከእንቅልፍ ሳልነቃ ውሃ ሲረጩኝ እንደ ኤሌክትሪክ ይነዝረኛል፡፡ ሁለት ሦስት ቀን ሲደጋግሙኝ፣ ገና ድምፃቸውን ስሰማ መነሳት ጀመርኩ፡፡ ፀሎትና ምህላው እስከ ጥዋቱ አስራ ሁለት ሰዓት ይደረጋል፤ ከዛ ወደ ፀበል።
ገዳሙን ቅጥር ግቢ በደንብ ለማማወቅ እየተዟዟርኩ ማየት ጀመርኩ፡፡ የአርሴማ ገዳም በሃገራችን እንዳሉት አብዛኞቹ ገዳማት፣በተራራማ ቦታ ላይ ከየተመሰረተ ነው፡፡ የገዳሙ መስራችና አስተዳዳሪ
የሆኑት መነኩሴ፣ እድሜያቸው ሃምሳ ዓመት ቢሆን ነው፡፡ ገዳሙ በእውቀት እንዲለማ በደንብ አስበውበት እንደመሰረቱት ገዳሙ አፍ አውጥቶ ይናገራል፡፡ ከመሰረቱት
❤1👍1