ነገ ምን አይነት ችግር ይገጥመኝ ይሆን ብየ ፈርቻለሁ ተጨንቂያለሁ። ቢሆንም ግን ከፍሪ ታውን በመውጣቴ እና ድጋሚ ወታደር ከመሆን ስላመለጥኩ ደስ ብሎኛል። በዚህ ተፅናናሁ፤ የቀረኝን ሩዝ ከሻንጣየ በማውጣት መብላት ጀመርኩ። ከ እኔ ትንሽ ራቅ ብሎ አንዲት ሴት ከሰባት አመት የማይበልጡ ወንድ እና ሴት
ልጆቿ ጋር ተቀመጣለች፡፡ ሌሎች ሰዎችን ላለመረበሽ ቀስ ብላ ለልጆቿ ተረት ታንሾካሽካለች። እጆቿን ስታንቀሳቅስ ልጅ ሁኜ ብዙ ጊዜ የሰማሁት አንድ ተረት ትዝ አለኝ።
ለሊት ነበር እና እሳት ዳር ቁጭ ብለን እጆቻችንን ወደ ነበልባሉ እያስጠጋን እየሞቅን ተረት እናዳምጣለን። ጨረቃ እና
ኮኮቦች ሲርቁ እናያለን፡፡ ቀይ ፍም ፊታችንን ሲያበራ ጭሱ ወደ
ሰማይ ተግተልትሎ ይወጣ ነበር። ከ ጓደኞቼ የአንዱ አያት የሆነው አባ ሲሳይ በዛ ምሽት ብዙ ተረቶችን ነግሮናል። ግን
የመጨረሻ ተረቱን ሲነግረን ደጋግሞ “ ይሄ በጣም ጠቃሚ ተረት ነው” ይል ነበር። ጎሮሮውን ጠራረገና ጀመረ።
“ዝንጀሮ ለመግደል ወደ ጫካ የወረደ አዳኝ ነበር። ዘወር ዘወር ብሎ ሲቃኝ የዛፍ ቅርንጫፍ ላይ ተደላድሎ የተቀመጠ ዝንጀሮ አየ።ዝንጀሮው የአዳኙ ኮቴ በደረቅ ቅጠሎች ሲያልፍ ድምፅ ቢያሰማም እስኪጠጋው ድረስ ብዙም ትኩረት አልሰጠውም::አዳኙ ዝንጀሮ በደንብ ወደ ሚታይበት ቦታ ሲደርስ መሳሪያውን
አዘጋጅቶ አነጣጠረ፡፡ ምላጩን ከመሳቡ በፊት ግን ዝንጀሮው እንዲህ ሲል ተናገረ:
ከተኮስክብኝ እናትህ ትሞታለች ፤ ካልተኮስክ ደግሞ አባትህ ይሞታል።” ዝንጀሮው ተስተካክሎ ተቀመጠ እና ምግቡን ማለመጥ፣ እራሱን ማከክ እና ሆዱን ማሻሸት ቀጠለ።
አዳኙ አንተ ብትሆን ምን ታደርግ ነበር?”
እኔ በአደኩበት መንደር ይሄ ተረት ለወጣቶች በአመት አንዴ ይነገራል። ተረት ተናጋሪው ሽማግሌ ተረቱን ከተናገረ በኋላ
ይህን ለመመለስ የሚያስቸግር ጥያቄ በህፃናቱ ወላጆች ፊት ነበር የሚያቀርበው። ሁሉም ልጆች አንድ በአንድ መልሳቸውን እንዲያቀረቡ ይጠየቃሉ። ወላጆቻቸው ከጎናቸው ስለሚሆኑ አንድም ልጅ መልሶ አያውቅም:: ተረት ተናጋሪውም መልሱን
ተናግሮ አያውቅም:: በእንደዚህ አይነት ስብስብ መልስ እንድሰጥ ስጠየቅ ሁሌም መልሴ ላስብበት ነበር። አጥጋቢ መልስ
አልነበረም::በእነዚህ ስብስቦች እኔ እና ጓደኞቼ ወላጆቻችንን ከሞት የሚያስቀር መልስ ለማግኘት የተለያዩ መልሶችን እናስብ ነበር።ግን አንድም አልነበረም:: ዝንጀሮ ከተውነው አንድ ሰው
ይሞታል፤ ዝንጀሮን ከገደልነው ደግሞ ሌላ ሰው ይሞታል።ያ ምሽት ግን በአንድ መልስ ተስማማን ግን ተቀባይነት
አላገኘም:: አባ ሲሳይን አዳኙ እኛ ከሆን ዝንጀሮዎች ለማደን አንወጣም ብለን ነገርናቸው:: “ለአደን የሚሆኑ ሌሎች እንስሳት ብለን ነገርናቸው።
ለምሳሌ አጋዘን “በፍፁም ይሄ ተቀባይነት የሌለው መልስ ነው” አሉ:: መሳሪያውን አነጣጥሮ ውሳኔ ስለቀረው ሰው ነው የምናወራው” አሉ የወይን እቃቸውን ከፍተው ከመጠጣታቸው በፊት ፈገግ
አሉ።
የሰባት ዓመት ልጅ እያለሁ ለዚህ ጥያቄ መልስ ነበረኝ። እናቴ ምን ይሰማታል በሚል ግን ለማንም ተናግሬው አላውቅም:: ለራሴ የደመደምኩት ግን አዳኙ ብሆን ዝንጀሮውን እገድለው እና
ሌሎች አዳኞች በእንደዚህ አይነት ቅርቃር ውስጥ እንዳይገቡ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እታደጋቸው ነበር።
✨ተፈፀመ ✨
ውድ #የአትሮኖስ ቻናል ተከታታዬቼ #የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ ይህን ይመስላል ብዙዎቻቹ አስተያየታችሁን በየክፍሉ ሰታችሁኛል የተመቸውም ያልተመቸውም አለ በኔ በኩል ያለኝን አስተያየት በየግል ስልክ ነበር አሁን ላይ ጠቅለል ሳደርገው ፅሁፉ በጣም የተመቸኝ እውነተኛ ታሪክ ነው ለዛም ነው ለናተ ያቀረብኩት #ያልተመቸኝ ነገር ከናንተ የመጣ ነገር ባይኖርም #ተርጓሚው ላይ ቅሬታ አለኝ ሲተረጎም የቃላት አጠቃቀም ላይ ለኛ ትርጉሙን የሚያዛባ አንዳንዴ ከሌላ ቋንቋ ወደእኛ ቀጥታ ሲተሮገም ስሜት የማይሰጡ አረፍተ ነገሮች አሉ እነሱ በዚ ታሪክ ላይ ብዙ አጋጥመውኛል አንዳንዴ የታሪክ ፍሰቱም መዘባረቅ ነበረበት እኔም ባለችኝ አቅም ለማስተካከል ሞክሪያለው...አስቲ እናንተም በታሪኩ ላይ እንዲሁም ከላይ ባነሳሁት ላይ ያላችሁን አስተያየት አድርሱኝ።
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ልጆቿ ጋር ተቀመጣለች፡፡ ሌሎች ሰዎችን ላለመረበሽ ቀስ ብላ ለልጆቿ ተረት ታንሾካሽካለች። እጆቿን ስታንቀሳቅስ ልጅ ሁኜ ብዙ ጊዜ የሰማሁት አንድ ተረት ትዝ አለኝ።
ለሊት ነበር እና እሳት ዳር ቁጭ ብለን እጆቻችንን ወደ ነበልባሉ እያስጠጋን እየሞቅን ተረት እናዳምጣለን። ጨረቃ እና
ኮኮቦች ሲርቁ እናያለን፡፡ ቀይ ፍም ፊታችንን ሲያበራ ጭሱ ወደ
ሰማይ ተግተልትሎ ይወጣ ነበር። ከ ጓደኞቼ የአንዱ አያት የሆነው አባ ሲሳይ በዛ ምሽት ብዙ ተረቶችን ነግሮናል። ግን
የመጨረሻ ተረቱን ሲነግረን ደጋግሞ “ ይሄ በጣም ጠቃሚ ተረት ነው” ይል ነበር። ጎሮሮውን ጠራረገና ጀመረ።
“ዝንጀሮ ለመግደል ወደ ጫካ የወረደ አዳኝ ነበር። ዘወር ዘወር ብሎ ሲቃኝ የዛፍ ቅርንጫፍ ላይ ተደላድሎ የተቀመጠ ዝንጀሮ አየ።ዝንጀሮው የአዳኙ ኮቴ በደረቅ ቅጠሎች ሲያልፍ ድምፅ ቢያሰማም እስኪጠጋው ድረስ ብዙም ትኩረት አልሰጠውም::አዳኙ ዝንጀሮ በደንብ ወደ ሚታይበት ቦታ ሲደርስ መሳሪያውን
አዘጋጅቶ አነጣጠረ፡፡ ምላጩን ከመሳቡ በፊት ግን ዝንጀሮው እንዲህ ሲል ተናገረ:
ከተኮስክብኝ እናትህ ትሞታለች ፤ ካልተኮስክ ደግሞ አባትህ ይሞታል።” ዝንጀሮው ተስተካክሎ ተቀመጠ እና ምግቡን ማለመጥ፣ እራሱን ማከክ እና ሆዱን ማሻሸት ቀጠለ።
አዳኙ አንተ ብትሆን ምን ታደርግ ነበር?”
እኔ በአደኩበት መንደር ይሄ ተረት ለወጣቶች በአመት አንዴ ይነገራል። ተረት ተናጋሪው ሽማግሌ ተረቱን ከተናገረ በኋላ
ይህን ለመመለስ የሚያስቸግር ጥያቄ በህፃናቱ ወላጆች ፊት ነበር የሚያቀርበው። ሁሉም ልጆች አንድ በአንድ መልሳቸውን እንዲያቀረቡ ይጠየቃሉ። ወላጆቻቸው ከጎናቸው ስለሚሆኑ አንድም ልጅ መልሶ አያውቅም:: ተረት ተናጋሪውም መልሱን
ተናግሮ አያውቅም:: በእንደዚህ አይነት ስብስብ መልስ እንድሰጥ ስጠየቅ ሁሌም መልሴ ላስብበት ነበር። አጥጋቢ መልስ
አልነበረም::በእነዚህ ስብስቦች እኔ እና ጓደኞቼ ወላጆቻችንን ከሞት የሚያስቀር መልስ ለማግኘት የተለያዩ መልሶችን እናስብ ነበር።ግን አንድም አልነበረም:: ዝንጀሮ ከተውነው አንድ ሰው
ይሞታል፤ ዝንጀሮን ከገደልነው ደግሞ ሌላ ሰው ይሞታል።ያ ምሽት ግን በአንድ መልስ ተስማማን ግን ተቀባይነት
አላገኘም:: አባ ሲሳይን አዳኙ እኛ ከሆን ዝንጀሮዎች ለማደን አንወጣም ብለን ነገርናቸው:: “ለአደን የሚሆኑ ሌሎች እንስሳት ብለን ነገርናቸው።
ለምሳሌ አጋዘን “በፍፁም ይሄ ተቀባይነት የሌለው መልስ ነው” አሉ:: መሳሪያውን አነጣጥሮ ውሳኔ ስለቀረው ሰው ነው የምናወራው” አሉ የወይን እቃቸውን ከፍተው ከመጠጣታቸው በፊት ፈገግ
አሉ።
የሰባት ዓመት ልጅ እያለሁ ለዚህ ጥያቄ መልስ ነበረኝ። እናቴ ምን ይሰማታል በሚል ግን ለማንም ተናግሬው አላውቅም:: ለራሴ የደመደምኩት ግን አዳኙ ብሆን ዝንጀሮውን እገድለው እና
ሌሎች አዳኞች በእንደዚህ አይነት ቅርቃር ውስጥ እንዳይገቡ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ እታደጋቸው ነበር።
✨ተፈፀመ ✨
ውድ #የአትሮኖስ ቻናል ተከታታዬቼ #የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ ይህን ይመስላል ብዙዎቻቹ አስተያየታችሁን በየክፍሉ ሰታችሁኛል የተመቸውም ያልተመቸውም አለ በኔ በኩል ያለኝን አስተያየት በየግል ስልክ ነበር አሁን ላይ ጠቅለል ሳደርገው ፅሁፉ በጣም የተመቸኝ እውነተኛ ታሪክ ነው ለዛም ነው ለናተ ያቀረብኩት #ያልተመቸኝ ነገር ከናንተ የመጣ ነገር ባይኖርም #ተርጓሚው ላይ ቅሬታ አለኝ ሲተረጎም የቃላት አጠቃቀም ላይ ለኛ ትርጉሙን የሚያዛባ አንዳንዴ ከሌላ ቋንቋ ወደእኛ ቀጥታ ሲተሮገም ስሜት የማይሰጡ አረፍተ ነገሮች አሉ እነሱ በዚ ታሪክ ላይ ብዙ አጋጥመውኛል አንዳንዴ የታሪክ ፍሰቱም መዘባረቅ ነበረበት እኔም ባለችኝ አቅም ለማስተካከል ሞክሪያለው...አስቲ እናንተም በታሪኩ ላይ እንዲሁም ከላይ ባነሳሁት ላይ ያላችሁን አስተያየት አድርሱኝ።
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#ባርቾ
:
:
#በሕይወት_እምሻው
በ12 ዓመቴ...ስቅስቅ ብዬ» አልቅሼ ስጨርስ ፣ በለቅሶ ይባስ የጠቋቆረ ጥቁር ፊቴን በቀኝ እጄ አይበሉባ እያሻሸሁ ወደ ቤት ስገባ ፣ እማዬን በር ላይ አገኘኋት: :
“ምን፣ ሆንሽ ባርቾ? ... ምነው?”
“ምንም! ” አልኳት ፡ : የደረሰብኝ ነገር ደግሞ ማውራቱ ይበልጥ የሚ ያስለቅሰኝ መስኰ ስለተሰማኝ : :
“ምን... ምንም ትይኛለሽ? ስታለቅሺ አልነበርም?” እማማ ተቆጣች ፡ :
“ትምህርት፥ ቤት ...” አልኩ አልቅሼ የጨረስኩት የመሰኝ እንባዬ እንደ
አዲስ ዐይኔ ውስጥ ሲሞላ እየተሰማኝ ፡ :
“ምን ሆንሽ .. ? ከማን ጋር ተጣካሽ?”
“አማርኛ አስተማሪ ... ቲቸር ስንሻው ...”
“ገረፈሽ ...? ጎሽ! የቤት ሥራ ሳትሰሪ ሄደሽ ገርፎሽ ነው አይደለም?
ደግ አደረገ፡”
“አይደለም አረ... እኔ የቤት ስራዬን ሰርቻለሁ ...”
አህስ... ስትርብሺ ዐይቶሽ ነው አይደለም? እያስተማረ ስቶረብሺ? ነይ
እንዲውም እኔም እጨምርልሻለሁ!” አለች እማዬ ቱግ እያለች ፡ :
አሁን ቀበቶ ፍለጋ ወደ ጎዳ ስትገባ ዐየሁና ጮክ ብዬ፣ አይደለም
እማዬ... እግዚአብሔርን፣... የገና ድራማ አትሠሪም ብሎኝ ነው አልኳት ፣ ስር ስሯ እየተከተልኳት።
ቀበቶውን፣ መፈለጓን ትታ ዞር ብላ አየችኝና ፣ “የገና ምን... ምን አትይም
ብሎኝ ነው? ” ብላ ጠየቀችኝ : :
“የገና ድራማ አትሰሪም ብሎኝ ነው እማዬ” አልኳት : :
ምንድነው ደግሞ የገና ድራማ?”
ባለፈው... ለገና በዓል የክርስቶስ፣ መወለድ በድራማ ትሰራላኝሁ ተብለናል ብዬ ከብሩኬ ጋር ሳጠና አልነበረም እማዬ?”
"ያ ... ሁሉንም በቃሌ መያዝ አለብኝ ስትይው የነበረው ነው እሱ? ”
“አዎ... እማዬ: :
“ታዲያ ፈቅዶልሽ አይደለም እንዴ አጥኚ የተባልሽው?”
“አዎ... እማዬ” አልኳት ፣ እንባዬ ሲመለስ እየተሰማኝ : :
“እና ታዲያ ምንድነው አትሰሪም ያለሽ አሁን?”
“አትሰሪም አትሰሪም አይደለም እኮ ያለኝ ” አልኩ ለቅሶዬን ጀምሬ : :
“ልጅቷ ያማታል እንዴ ...? ምንድነው የምትቀባጥሪው? አትሰሪም አለኝ
አላልሽም አሁን?” አለች እማዬ ቁጣዋ ተመልሶ : :
እኔ የፈለኩት እመቤቴ ማርያምን፣ ሆኜ መስራት ነበር ፡ : ሳጠና የነበረው እኮ የእመቤቴ ማርያምን፣ ነው ... እሱ ግን...
“እሱ ግን…? ምን አለሽ ታድያ ? ”
“እሱ ግን ቲቸሮች ሁኑ ተነጋግረንበት ነበር : :አንቺ በደንብ ብታጠኚውም ጥቁር ስለሆንሽ ማርያምን፣ ሆነሽ መስራት አትችይም : :
ሩት ናት ማርያምን የምትሆነው አለ” ብዬ ለቅሶዬን በነጻነት አድምቄ ጀመርኩት ፡ :
እማዬ ካሁን አሁን ተሰምቷት መጥታ እቅፍ ታደርገኝና ፣ እምባዬን ታብሰውና ፣
የሚይረባ! የኔ ልጅ ናት ማርያምን፤ ሆና የማትሰራው?
ነገውኑ ከአባትሽ ጋር ሄደን ለዲሪክተሩ ነገርነ ነው የምናስባርረው... አይዞሽ
ልጄ” ትለኛለች ብዬ ስጠብቅ ፣
“እውነቱን ነዋ! እስቲ የእመቤቴን ምስል
ዕይው! ምኗ ነው ከቶ አንቺን የሚመስል? አስተማሪሽ የሚልሽን፣ ስሚ ! ልክ ነው!” ብላ፤ ወደ ኩሽና ገባች: :
የዛን ዕለት እመቤቴ ማርያምን፣ ሆኜ ለመጫወት የነበረኝን ጉጉት ባጭር
የቀጩትን “ቲቸሮቼን፡” ፣ ድራማውን፤ በማጥናት ከእሷ 0ሥር እጅ
ብሻልም ቀይና ሰልካካ ስለሆነች ብቻ ማርያምን ሁኚ ተብላ የተመረጠችውን፣
ሩትን፣ ካልጠፋ ቕላት ጥቁር አድርጎ የፈጠረኝን፣ ፈጣሪንም በአንድነት
አማረርኩ ፡ :
ምሽት ላይ ፤ እኔ ፣ ትልቋ እና ቀይዋ እህቴ ፣ ቀዩ ወንድሜ ፣ ጠይሙ አባቴና በጣም ቀይዋ እናቴ ተሰብስበን ቴሌቪዥን እናያለን። ለነገሩ ቴሌቪዥኑን የሚያዩት እነሱ እንጂ እኔ የማየው እነሱንና ቅላታቸውን፣ ነው : : እያየኋቸው እናደሚከተለው አሰባለሁ ፣
...እስቲ አሁን በእመቤቴ ፣ እኔ ከየት መጥቼ ጠቆርኩ? አባቴ ጠይም
ነው ፤ እናቴ በጣም ቀይ ናት ፡ : ሁለቱ ሲቀላቀሉ እንደ እህቴ ስህንና እንደ ወንድሜ ብሩክ ቀይ ሰው ባይፈጥሩ እንኳን እንደኔ ጠቋራ ሰው መፍጠር ነበረባቸው? የእህቴስ ይሁን፡ : ሴት ናት : : በዛ ላይ ታላቄ ናት ፡ ይሁንላት ትቅላ ፤ ግን አሁን እኔ ከምጠቁር ወንድሜ ቢጠቁር ምናለበት እስቲ…? ደግሞ እኮ እኔ ብቻ አይደለሁም : :ሁሉም ሰው የሚለው ነገር
ነው : : እማዬ ሁል ጊዜ ብሩክንና እኔን ይዛን ወጣ ስትል ፣
አይ ወይዘሮ ኤልሳቤጥ! ሴቷን ልጅ አጥቁረሽ ቅላትሽን፣ ሁኩ ወንዱ ልጅ
ላይ አባከንሽው! መልክ ለወንድ ልጅ ምን ያደርጋል አሁን? አሄሄ!” ይላሉ
እኔ እንዲህና እንዲያ ሳስብ ቴሌቪዢኑ ላይ ጓድ መንግስቱ ሐይለማርያም
የዛንቢያውን፣ ፕሬዝዳንት ኬኔት ካውንዳን፤ ሲቀበሉ የሚያሳይ ምስል መጣ ፡ :
መንግስቱ ኃይለማርያም ቴሌቪዥን ላይ ፣ በመጣ ቁጥር የሚቀልዱብኝ ቀልድ
እስኪጅምር ጠበቅኩ ፤ “መንጌ እኮ አባትሽ ነው” ሊሉኝ ነው ።ጠበቅኳቸው።
እህቴ ቀደመችና ፣ ይሄውልሽ ሜሮን አጎትሽ አባትሽን ለመጠይቅ አዲስ
አበባ መጣ!” ሁኩም ሣቁ።
እኔ ግን ነጭ መሃረብ እያርገበገበ ከአውሮፕላን የሚወርደውን፣ “አጎቴ፣” ኬኔት ካውንዳን እየያየሁ እግዚአብሔር ከነነጭ መሃረቡ በአውሎ ንፋስ ጥ...ር...ግ አድርጎ ወደ መጣበት ቢመልሰው እቸተመኘሁ ከእንባዬ ተናነቅሁ : : ደግሞ በዚህ ጥቁርቱ ላይ ነጭ መዓርብ የሚይዘው አማረብኝ ብሎ ነው? ...ወይስ ከሩቅ እንዲታይ? አንጀቴን
አሳረረው : :
“ዕያት ... ዕያት ... በሸቀች! በሸቀች” ይላሉ እየተቀባበሉ።
“አትናደጂ! ይባስ ያጠቁርሻል” አለ
ብሩክ ፣ አጠገቤ መጥቶ እየሣቅ ።
የማርያም አጃቢ ሆኜ የገናውን ድራማ በሰራሁ በሁለት ሳምንቴ አስራ ሶስት
ዓመት ሞላኝ : : ሁሌም ለልደቴ እንደምናደርገው ድፎ ዳቦ ዳቦና
ሻማ ፣ ከተወሰኑ የለስላሳ ጠርሙሶች ጋር ይዘን የልደት ፎቶ ልንነሳ ከእማዬ ፣ አባዬ ፣ ስህንና ብሩክ ጋር አስረስ ፎቶ ቤት ሄድን ጋሽ አስርስ ይወደኛል ፤ “ኮረሪማ!” ይለኛል ገና ከሩቅ ሲያየኝ : :
“ኮረሪማ አረጀሽ በቃ! ትልቅ ሰው ... ትልቅ ኮረሪማ” አለኝ፤ ገና ከመግባታችን። ሣቅኹ ።መጣና እቅፍ አድርጎ ከሳመኝ በኋላ ለፎቶው መዘጋጀት ጀመርኩ።
ጋሽ አስርስ ሁሉን ነገር አሰናድቶ ለማንፀሳት ሲያነጣጥር አባቴ ጮክ አለና
“አስረስ ፣ ይህን መጋረጃ ቀይረው እንጂ ” አለው።
“የቱን? ” አለ ጋሽ አስረስ ፣ ካሜራው፣ ከእነ አንትገ ማንጠልጠያው፥
ከፊቱ ወደ ደረቱ፥ እየመለሰ ።
“ከኋላዋ ያለውን ጥቁር መጋርጃ!” አለ አባቴ : :
ኋላ ላይ ሻማው ፣ ጥርሷና ሚሪንዳው ብቻ ይወጣልህና ጉድ እንዳትሆን!” ሲለው ፤ ይወደኝ የመሰለኝ፤ ጋሽ አስረስ ከቀያዮቹ ቤተሰቦቼ ጋር ተደርቦ ሲስቅ ጠላሁት : :
።።።።።
በሃያ ሁለት ዓመቴ...
እንዲህ እንዲህ ሲብስ ሲብስ ፣ “ባርቾ እኮ ጭንቅላት ባይኖራት ጉዷ ነበር!
“አንቺ፤ ግን ሀበሻ ነሽ? ጋና እኮ ነው የምትመስይው!”
.
:
ሲሻል ደግሞ ፣ ብትቀላ ቆንጆ ነበረች፡ : እየተባልኩ፣ በቀያይ ቤተሰቦቼና ዘመዶቼ እየተቀለደብኝ ኖርኩ ፡ : በሃያ ሁለት ዓመቴም የትወና ጥበብ ተምሬ ጨርስኩና የጊዜውን የፊልም ሥራ በርከት ለመቋደስ ብዙ ቦታ ተመዝግቤ መፈተን ጀመርኩ። ከኮሌጅ ሰቅዬ
ነበር የተመረቕኩት ፣ ግን ደህና የፊልምም የቲያትርም የትወና ሥራ ማግኘት አልቻልኩም : : “በጣም አሪፍ ነው ፡ ፡ እናደውልልሻለን። ይሉኝና አይደውሉም።
ሌሎቹ ደግሞ ፣ ለትወና ሥራ አመልክቼ ፣ “ፐ! አንቺ በጣም ጎበዝ ተዋናይ ነሽ... ለምን፣ ማስተማር አትሞክሪም? ” ይሉኝና ያሰናብቱኛል። ነገሩ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ግልጥልጥ ያለልኝ ፤ ታሪኩንና ስክሪፕቱ
:
:
#በሕይወት_እምሻው
በ12 ዓመቴ...ስቅስቅ ብዬ» አልቅሼ ስጨርስ ፣ በለቅሶ ይባስ የጠቋቆረ ጥቁር ፊቴን በቀኝ እጄ አይበሉባ እያሻሸሁ ወደ ቤት ስገባ ፣ እማዬን በር ላይ አገኘኋት: :
“ምን፣ ሆንሽ ባርቾ? ... ምነው?”
“ምንም! ” አልኳት ፡ : የደረሰብኝ ነገር ደግሞ ማውራቱ ይበልጥ የሚ ያስለቅሰኝ መስኰ ስለተሰማኝ : :
“ምን... ምንም ትይኛለሽ? ስታለቅሺ አልነበርም?” እማማ ተቆጣች ፡ :
“ትምህርት፥ ቤት ...” አልኩ አልቅሼ የጨረስኩት የመሰኝ እንባዬ እንደ
አዲስ ዐይኔ ውስጥ ሲሞላ እየተሰማኝ ፡ :
“ምን ሆንሽ .. ? ከማን ጋር ተጣካሽ?”
“አማርኛ አስተማሪ ... ቲቸር ስንሻው ...”
“ገረፈሽ ...? ጎሽ! የቤት ሥራ ሳትሰሪ ሄደሽ ገርፎሽ ነው አይደለም?
ደግ አደረገ፡”
“አይደለም አረ... እኔ የቤት ስራዬን ሰርቻለሁ ...”
አህስ... ስትርብሺ ዐይቶሽ ነው አይደለም? እያስተማረ ስቶረብሺ? ነይ
እንዲውም እኔም እጨምርልሻለሁ!” አለች እማዬ ቱግ እያለች ፡ :
አሁን ቀበቶ ፍለጋ ወደ ጎዳ ስትገባ ዐየሁና ጮክ ብዬ፣ አይደለም
እማዬ... እግዚአብሔርን፣... የገና ድራማ አትሠሪም ብሎኝ ነው አልኳት ፣ ስር ስሯ እየተከተልኳት።
ቀበቶውን፣ መፈለጓን ትታ ዞር ብላ አየችኝና ፣ “የገና ምን... ምን አትይም
ብሎኝ ነው? ” ብላ ጠየቀችኝ : :
“የገና ድራማ አትሰሪም ብሎኝ ነው እማዬ” አልኳት : :
ምንድነው ደግሞ የገና ድራማ?”
ባለፈው... ለገና በዓል የክርስቶስ፣ መወለድ በድራማ ትሰራላኝሁ ተብለናል ብዬ ከብሩኬ ጋር ሳጠና አልነበረም እማዬ?”
"ያ ... ሁሉንም በቃሌ መያዝ አለብኝ ስትይው የነበረው ነው እሱ? ”
“አዎ... እማዬ: :
“ታዲያ ፈቅዶልሽ አይደለም እንዴ አጥኚ የተባልሽው?”
“አዎ... እማዬ” አልኳት ፣ እንባዬ ሲመለስ እየተሰማኝ : :
“እና ታዲያ ምንድነው አትሰሪም ያለሽ አሁን?”
“አትሰሪም አትሰሪም አይደለም እኮ ያለኝ ” አልኩ ለቅሶዬን ጀምሬ : :
“ልጅቷ ያማታል እንዴ ...? ምንድነው የምትቀባጥሪው? አትሰሪም አለኝ
አላልሽም አሁን?” አለች እማዬ ቁጣዋ ተመልሶ : :
እኔ የፈለኩት እመቤቴ ማርያምን፣ ሆኜ መስራት ነበር ፡ : ሳጠና የነበረው እኮ የእመቤቴ ማርያምን፣ ነው ... እሱ ግን...
“እሱ ግን…? ምን አለሽ ታድያ ? ”
“እሱ ግን ቲቸሮች ሁኑ ተነጋግረንበት ነበር : :አንቺ በደንብ ብታጠኚውም ጥቁር ስለሆንሽ ማርያምን፣ ሆነሽ መስራት አትችይም : :
ሩት ናት ማርያምን የምትሆነው አለ” ብዬ ለቅሶዬን በነጻነት አድምቄ ጀመርኩት ፡ :
እማዬ ካሁን አሁን ተሰምቷት መጥታ እቅፍ ታደርገኝና ፣ እምባዬን ታብሰውና ፣
የሚይረባ! የኔ ልጅ ናት ማርያምን፤ ሆና የማትሰራው?
ነገውኑ ከአባትሽ ጋር ሄደን ለዲሪክተሩ ነገርነ ነው የምናስባርረው... አይዞሽ
ልጄ” ትለኛለች ብዬ ስጠብቅ ፣
“እውነቱን ነዋ! እስቲ የእመቤቴን ምስል
ዕይው! ምኗ ነው ከቶ አንቺን የሚመስል? አስተማሪሽ የሚልሽን፣ ስሚ ! ልክ ነው!” ብላ፤ ወደ ኩሽና ገባች: :
የዛን ዕለት እመቤቴ ማርያምን፣ ሆኜ ለመጫወት የነበረኝን ጉጉት ባጭር
የቀጩትን “ቲቸሮቼን፡” ፣ ድራማውን፤ በማጥናት ከእሷ 0ሥር እጅ
ብሻልም ቀይና ሰልካካ ስለሆነች ብቻ ማርያምን ሁኚ ተብላ የተመረጠችውን፣
ሩትን፣ ካልጠፋ ቕላት ጥቁር አድርጎ የፈጠረኝን፣ ፈጣሪንም በአንድነት
አማረርኩ ፡ :
ምሽት ላይ ፤ እኔ ፣ ትልቋ እና ቀይዋ እህቴ ፣ ቀዩ ወንድሜ ፣ ጠይሙ አባቴና በጣም ቀይዋ እናቴ ተሰብስበን ቴሌቪዥን እናያለን። ለነገሩ ቴሌቪዥኑን የሚያዩት እነሱ እንጂ እኔ የማየው እነሱንና ቅላታቸውን፣ ነው : : እያየኋቸው እናደሚከተለው አሰባለሁ ፣
...እስቲ አሁን በእመቤቴ ፣ እኔ ከየት መጥቼ ጠቆርኩ? አባቴ ጠይም
ነው ፤ እናቴ በጣም ቀይ ናት ፡ : ሁለቱ ሲቀላቀሉ እንደ እህቴ ስህንና እንደ ወንድሜ ብሩክ ቀይ ሰው ባይፈጥሩ እንኳን እንደኔ ጠቋራ ሰው መፍጠር ነበረባቸው? የእህቴስ ይሁን፡ : ሴት ናት : : በዛ ላይ ታላቄ ናት ፡ ይሁንላት ትቅላ ፤ ግን አሁን እኔ ከምጠቁር ወንድሜ ቢጠቁር ምናለበት እስቲ…? ደግሞ እኮ እኔ ብቻ አይደለሁም : :ሁሉም ሰው የሚለው ነገር
ነው : : እማዬ ሁል ጊዜ ብሩክንና እኔን ይዛን ወጣ ስትል ፣
አይ ወይዘሮ ኤልሳቤጥ! ሴቷን ልጅ አጥቁረሽ ቅላትሽን፣ ሁኩ ወንዱ ልጅ
ላይ አባከንሽው! መልክ ለወንድ ልጅ ምን ያደርጋል አሁን? አሄሄ!” ይላሉ
እኔ እንዲህና እንዲያ ሳስብ ቴሌቪዢኑ ላይ ጓድ መንግስቱ ሐይለማርያም
የዛንቢያውን፣ ፕሬዝዳንት ኬኔት ካውንዳን፤ ሲቀበሉ የሚያሳይ ምስል መጣ ፡ :
መንግስቱ ኃይለማርያም ቴሌቪዥን ላይ ፣ በመጣ ቁጥር የሚቀልዱብኝ ቀልድ
እስኪጅምር ጠበቅኩ ፤ “መንጌ እኮ አባትሽ ነው” ሊሉኝ ነው ።ጠበቅኳቸው።
እህቴ ቀደመችና ፣ ይሄውልሽ ሜሮን አጎትሽ አባትሽን ለመጠይቅ አዲስ
አበባ መጣ!” ሁኩም ሣቁ።
እኔ ግን ነጭ መሃረብ እያርገበገበ ከአውሮፕላን የሚወርደውን፣ “አጎቴ፣” ኬኔት ካውንዳን እየያየሁ እግዚአብሔር ከነነጭ መሃረቡ በአውሎ ንፋስ ጥ...ር...ግ አድርጎ ወደ መጣበት ቢመልሰው እቸተመኘሁ ከእንባዬ ተናነቅሁ : : ደግሞ በዚህ ጥቁርቱ ላይ ነጭ መዓርብ የሚይዘው አማረብኝ ብሎ ነው? ...ወይስ ከሩቅ እንዲታይ? አንጀቴን
አሳረረው : :
“ዕያት ... ዕያት ... በሸቀች! በሸቀች” ይላሉ እየተቀባበሉ።
“አትናደጂ! ይባስ ያጠቁርሻል” አለ
ብሩክ ፣ አጠገቤ መጥቶ እየሣቅ ።
የማርያም አጃቢ ሆኜ የገናውን ድራማ በሰራሁ በሁለት ሳምንቴ አስራ ሶስት
ዓመት ሞላኝ : : ሁሌም ለልደቴ እንደምናደርገው ድፎ ዳቦ ዳቦና
ሻማ ፣ ከተወሰኑ የለስላሳ ጠርሙሶች ጋር ይዘን የልደት ፎቶ ልንነሳ ከእማዬ ፣ አባዬ ፣ ስህንና ብሩክ ጋር አስረስ ፎቶ ቤት ሄድን ጋሽ አስርስ ይወደኛል ፤ “ኮረሪማ!” ይለኛል ገና ከሩቅ ሲያየኝ : :
“ኮረሪማ አረጀሽ በቃ! ትልቅ ሰው ... ትልቅ ኮረሪማ” አለኝ፤ ገና ከመግባታችን። ሣቅኹ ።መጣና እቅፍ አድርጎ ከሳመኝ በኋላ ለፎቶው መዘጋጀት ጀመርኩ።
ጋሽ አስርስ ሁሉን ነገር አሰናድቶ ለማንፀሳት ሲያነጣጥር አባቴ ጮክ አለና
“አስረስ ፣ ይህን መጋረጃ ቀይረው እንጂ ” አለው።
“የቱን? ” አለ ጋሽ አስረስ ፣ ካሜራው፣ ከእነ አንትገ ማንጠልጠያው፥
ከፊቱ ወደ ደረቱ፥ እየመለሰ ።
“ከኋላዋ ያለውን ጥቁር መጋርጃ!” አለ አባቴ : :
ኋላ ላይ ሻማው ፣ ጥርሷና ሚሪንዳው ብቻ ይወጣልህና ጉድ እንዳትሆን!” ሲለው ፤ ይወደኝ የመሰለኝ፤ ጋሽ አስረስ ከቀያዮቹ ቤተሰቦቼ ጋር ተደርቦ ሲስቅ ጠላሁት : :
።።።።።
በሃያ ሁለት ዓመቴ...
እንዲህ እንዲህ ሲብስ ሲብስ ፣ “ባርቾ እኮ ጭንቅላት ባይኖራት ጉዷ ነበር!
“አንቺ፤ ግን ሀበሻ ነሽ? ጋና እኮ ነው የምትመስይው!”
.
:
ሲሻል ደግሞ ፣ ብትቀላ ቆንጆ ነበረች፡ : እየተባልኩ፣ በቀያይ ቤተሰቦቼና ዘመዶቼ እየተቀለደብኝ ኖርኩ ፡ : በሃያ ሁለት ዓመቴም የትወና ጥበብ ተምሬ ጨርስኩና የጊዜውን የፊልም ሥራ በርከት ለመቋደስ ብዙ ቦታ ተመዝግቤ መፈተን ጀመርኩ። ከኮሌጅ ሰቅዬ
ነበር የተመረቕኩት ፣ ግን ደህና የፊልምም የቲያትርም የትወና ሥራ ማግኘት አልቻልኩም : : “በጣም አሪፍ ነው ፡ ፡ እናደውልልሻለን። ይሉኝና አይደውሉም።
ሌሎቹ ደግሞ ፣ ለትወና ሥራ አመልክቼ ፣ “ፐ! አንቺ በጣም ጎበዝ ተዋናይ ነሽ... ለምን፣ ማስተማር አትሞክሪም? ” ይሉኝና ያሰናብቱኛል። ነገሩ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ግልጥልጥ ያለልኝ ፤ ታሪኩንና ስክሪፕቱ
👍1👏1
ን አንብቤው በመሪ ተዋናይነት ልሠራበት የተንሰፈሰፍኩት ፣ “የማይነጋ ሌሊት” የተሰኘ ፊልም ላይ ለመቀጠር ፈተናው፤ ከጨርስኩ በኋላ ነበር : : ፈተናዬን፣ እንደኔ አስተሳሰብ ፣ “በሚያስገርም ብቃት” ፤ እንደ አዘጋጁ አባባል ፣ “በሚደንቅ ችሎታ” ከጨረስኩ በኋላ ልወጣ ስል ፤ አዘጋጁ የቀኝ እጁን በ“ወደኔ ነይ” ዓይነት ሲወዘውዝ ዐየሁት
ሄድኩ ፡ :
“ሜሮን በጣም በጣም ጎበዝ ተዋናይት ነሽ”
“እግዜር ይስጥልኝ... በጣም ነው ካራክተሯን' የወደድኳት! ብሠራት፥ ደስ
ይለኛል” አልኩት : : ጎበዝ ስላለኝ ደስ ብሎኝ እየሣቅኹ: :
“እኔም ደስ ይለኝ ነበር... የእውነት ሁላችንም ደስ ይለን ነበር ፣ ግን
ትወና ከመቻልሽ ውጪ የሰላንም፣ ካራክተር በምንም አትመስይም” አለኝ፤ በደንብ እያየኝ።
“እንዴት? ... የካራክተሯን ገለፃ ሳነበው ደፋር ፣ ጠንካራና ቁጡ ነው የሚለው : :
እሱን፤ አላሳየሁህም? ”
እ... እሱንማ በደንብ ነው የሰራሽው ... ግን፤... እሱ አይደለም...”
“ታዲያ ምንድነው?”
“ካራክተሯ ቀይ ናት ፡ : ”
“አቤት”
“ሰላም ቀይ ናት : : ”
“የቱ ጋር ነው ቀይ ናት የሚለው? ገለጻው ላይ የሚለው ደፋር ፣ ጠንራካ እና ቁጡ ብቻ ነው...” አልኩት ደሜ እየፈላ ፡ :
“ሜሮን! ሰላም የኔ ፈጠራ ናት ፡ : ቀይ ናት ካልኩ ቀይ ናት ፡ : መሪ ተዋናይት ሆና ጥቁር እንድትሆን ጠብቀሽ ነበር...? እስኪ አስቢው ፓስተሩን..!” አለኝ፤ ፣ እሱም ንዴት ንዴት እያለው : :
በሐዘን ዝም ብዬ ዐየሁትና ጀርባዬን ሰጥቼው ወጣሁ : :
ግቢው በር ላይ ሰደርስ የአዘጋጁ ድምጽ ሲጠራኝ ሰማሁ : : በአሸናፊነት ጮክ
ብዬ ተነፈስኩና ዞር አልኩ ፡ : አጠገቡ ስደርስ ፣ “ ይሄውልሽ
ሜሮን ፣ አንቺ ፣ ጎበዝ ተዋናይት ነሽ ...
እና ለፊልምህ ጎበዝ ተዋናይ እንጂ ቀይ ሰው እንደምትፈልግ አሁን ገባህ?” አልኩት ፣ ኩራትም ደስታም አያቁነጠነጠኝ : :
“እ... ይህን የመሰለ ታለንት ዌስትድ'” ከሚሆን ለምን የእልፌን፣ ካራክተር
አትሠሪውም ብዬ ነው...”
ግራ ገብቶኝ ዐየሁትና ፣ እልፌ ደሞ ማናት? እዚሁ ፊልም ውስጥ
ናት?” አልኩት : :
“አዎ... የእነ ሰላም ሰራተኛ ናት ፡ : ግን፤ በጣም ብዙ ሮል ነው ያላት...ዕይው ከፈከግሽ ስክራፕቱን፣“...” ብሎ ከያዛቸው ወረቀቶች መሃከል የተወሰኑ፥ ለመምረጥ ሲዋከብ ሳየው ነገሩ ሁኩ ቅዠት መሰኝ ፤
እንዴት፥ ከግቢው እንደወጣሁ ሳላስተውል ፤ ትንሽ ራቅ እንዳልኩ ከእንባዬ ጋር እየታገልኩ ስልኬን አወጣሁና ውጪ ሀገር ላለችው ታላቅ እህቴ የሚከተለውን የፅሁፍ መልዕክት ላኩላት : :
እንዴት ነሽ ስህን? ባለፈው ያልሽኝን፣ በዐሥራ አምስት ቀን ቆዳ የሚያቀላውን ክሬም ቶሎ ላኪልኝ አደራ !!
✨አልቋል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ሄድኩ ፡ :
“ሜሮን በጣም በጣም ጎበዝ ተዋናይት ነሽ”
“እግዜር ይስጥልኝ... በጣም ነው ካራክተሯን' የወደድኳት! ብሠራት፥ ደስ
ይለኛል” አልኩት : : ጎበዝ ስላለኝ ደስ ብሎኝ እየሣቅኹ: :
“እኔም ደስ ይለኝ ነበር... የእውነት ሁላችንም ደስ ይለን ነበር ፣ ግን
ትወና ከመቻልሽ ውጪ የሰላንም፣ ካራክተር በምንም አትመስይም” አለኝ፤ በደንብ እያየኝ።
“እንዴት? ... የካራክተሯን ገለፃ ሳነበው ደፋር ፣ ጠንካራና ቁጡ ነው የሚለው : :
እሱን፤ አላሳየሁህም? ”
እ... እሱንማ በደንብ ነው የሰራሽው ... ግን፤... እሱ አይደለም...”
“ታዲያ ምንድነው?”
“ካራክተሯ ቀይ ናት ፡ : ”
“አቤት”
“ሰላም ቀይ ናት : : ”
“የቱ ጋር ነው ቀይ ናት የሚለው? ገለጻው ላይ የሚለው ደፋር ፣ ጠንራካ እና ቁጡ ብቻ ነው...” አልኩት ደሜ እየፈላ ፡ :
“ሜሮን! ሰላም የኔ ፈጠራ ናት ፡ : ቀይ ናት ካልኩ ቀይ ናት ፡ : መሪ ተዋናይት ሆና ጥቁር እንድትሆን ጠብቀሽ ነበር...? እስኪ አስቢው ፓስተሩን..!” አለኝ፤ ፣ እሱም ንዴት ንዴት እያለው : :
በሐዘን ዝም ብዬ ዐየሁትና ጀርባዬን ሰጥቼው ወጣሁ : :
ግቢው በር ላይ ሰደርስ የአዘጋጁ ድምጽ ሲጠራኝ ሰማሁ : : በአሸናፊነት ጮክ
ብዬ ተነፈስኩና ዞር አልኩ ፡ : አጠገቡ ስደርስ ፣ “ ይሄውልሽ
ሜሮን ፣ አንቺ ፣ ጎበዝ ተዋናይት ነሽ ...
እና ለፊልምህ ጎበዝ ተዋናይ እንጂ ቀይ ሰው እንደምትፈልግ አሁን ገባህ?” አልኩት ፣ ኩራትም ደስታም አያቁነጠነጠኝ : :
“እ... ይህን የመሰለ ታለንት ዌስትድ'” ከሚሆን ለምን የእልፌን፣ ካራክተር
አትሠሪውም ብዬ ነው...”
ግራ ገብቶኝ ዐየሁትና ፣ እልፌ ደሞ ማናት? እዚሁ ፊልም ውስጥ
ናት?” አልኩት : :
“አዎ... የእነ ሰላም ሰራተኛ ናት ፡ : ግን፤ በጣም ብዙ ሮል ነው ያላት...ዕይው ከፈከግሽ ስክራፕቱን፣“...” ብሎ ከያዛቸው ወረቀቶች መሃከል የተወሰኑ፥ ለመምረጥ ሲዋከብ ሳየው ነገሩ ሁኩ ቅዠት መሰኝ ፤
እንዴት፥ ከግቢው እንደወጣሁ ሳላስተውል ፤ ትንሽ ራቅ እንዳልኩ ከእንባዬ ጋር እየታገልኩ ስልኬን አወጣሁና ውጪ ሀገር ላለችው ታላቅ እህቴ የሚከተለውን የፅሁፍ መልዕክት ላኩላት : :
እንዴት ነሽ ስህን? ባለፈው ያልሽኝን፣ በዐሥራ አምስት ቀን ቆዳ የሚያቀላውን ክሬም ቶሎ ላኪልኝ አደራ !!
✨አልቋል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍3
#የድሃ_ልደት
መሬት ላይ እየተኙ እግር ስር እየወደቁ
ኑሮ በሚባል ከስክስ ጫማ ተረግጠው እየደቀቁ፣
“አለን ይመስገን ይላሉ
በሰው ጥላ ስር እየዋሉ፡፡
ምቹ ማረፊያ ያጣን ተንሳፋፊ ብናኞች
ፍርፋሪ ፍለጋ የሰው ፊት ምናይ ትንኞች ፧
ይኼንም ኑሮ አልነውና
አንድ ቀን እንኳ ሳይደላን አንድ ቀን እንኳ ሳንዝናና፣
ስጋ ውስጥ ነብስ ተፈጥሮ
በእስትንፋስ ዕድሜ ተቆጥሮ ፤
ሃምሳ አመት ሞላው ይባላል
ሰው በቁጥር ይደለላል፡፡
ወዲያ የድሃ ልደት፣
ወዲያ የደሃ ኑሮ!
የቁጥር ብቻ ቋጠሮ፡፡
🔘ሙሉቀን🔘
መሬት ላይ እየተኙ እግር ስር እየወደቁ
ኑሮ በሚባል ከስክስ ጫማ ተረግጠው እየደቀቁ፣
“አለን ይመስገን ይላሉ
በሰው ጥላ ስር እየዋሉ፡፡
ምቹ ማረፊያ ያጣን ተንሳፋፊ ብናኞች
ፍርፋሪ ፍለጋ የሰው ፊት ምናይ ትንኞች ፧
ይኼንም ኑሮ አልነውና
አንድ ቀን እንኳ ሳይደላን አንድ ቀን እንኳ ሳንዝናና፣
ስጋ ውስጥ ነብስ ተፈጥሮ
በእስትንፋስ ዕድሜ ተቆጥሮ ፤
ሃምሳ አመት ሞላው ይባላል
ሰው በቁጥር ይደለላል፡፡
ወዲያ የድሃ ልደት፣
ወዲያ የደሃ ኑሮ!
የቁጥር ብቻ ቋጠሮ፡፡
🔘ሙሉቀን🔘
#የታካሚው_ማስታወሻ(ህመም አልባው በሽታ)
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ(MD)
1.ቅድመ ታሪክ
ከአንድ ዓመት ስራ መፍታት በኋላ፣ እንደገና ስራ ልጀምር ነው። በማኔጅመንት ሁለተኛ ድግሪና ከአስር ዓመት በላይ የስራ ልምድ አለኝ። ያለ ስራ በቆየሁበት ግዜ፣ ያጠራቀምኩትን ገንዘብ ጨርሼ
ንብረቶቼን ሸጥኩ፡፡ አሁን መኪናዬን ለመሸጥ በማሰብ ላይ ሳለሁ ስራ
አገኘሁ፡፡ ከባድ ግዜ ነበር፡፡ ንብረት ከማጣት በተጨማሪ፣ የስነ ልቦና ጉዳቱ ይሄ ነው ሚባል አይደለም፡፡ በራሴ ያለኝ መተማመን በከፍተኛ ደረጃ አሽቆልቁሏል፡፡ ከዚህ በፊትም፣ በተመሳሳይ ስራ ለቅቄ እስክፀፀት
ተቸግሬ አውቃለሁ፡፡ ሁለተኛ ብዬ ለራሴ ቃል ገብቼ ነበር፡፡ ቃሌን መጠበቅ አቅቶኝ፣ ይኸው ለአመት ተንከራተትኩ፡፡
የመጨረሻው ድርጅቴ በጣም ጥሩ ክፍያን ይከፍለኝ ነበር፡፡በተጨማሪም፣ ለሙያዬ እድገት የሚረዱኝ የተለያዩ የስልጠና እድሎችን በሃገር ውስጥና በውጪ ሃገራት ያመቻችልኝ ነበር፡፡ በጣም ደስተኛ ሆኜ ነበር፡፡ ብዙ እንደምቆይበት ተሰምቶኝ ነበር፡፡ ከተወሰነ ግዜ በኋላ ግን፣ሰራተኛው የተከፋፈለና በየቀኑ የሚካሰስ እንደሆነ እየተሰማኝ መጣ፡፡እኔ ደግሞ እንደ አስተዳደር ስራዬ መዳኘት ነው፤ አንዱን በዳይ፣አንዱን ተበዳይ አድርጎ መፍረድ፡፡ እኔ ደግሞ፣ ከመፍረድና ከመቅጣት ይልቅ፣ ችግሩን በማስታረቅ መፍታት የተሻለ መስሎ ተሰማኝ፡፡ እንደዛ ሞከርኩ። አይሳካም፡፡ ጭራሽ ወደኋላ አምስት፣ አስር ዓመት
ተመልሰው፣ “እርሱ/እርሷ፣ ባለፈውም እንዲህ በድሎኝ/ላኝ፣” እያሉ ሌላ
የክስ ቱባ ይተረትራሉ።
ጓደኛ ሆኜ ቀርቤያቸው፣ መሰረታዊ የፀባቸውን መንስኤ ለማወቅ
ሞከርኩ፡፡ ከአሉባልታ የዘለለ፣ ይሄ ነው የሚባል የከፋ ነገር የላቸዉም፡፡ክሶቻቸው ከጥርጣሬና፣ ሳይቀድመኝ ልቅደመው ከማለት የሚመነጩ ናቸው። እኩል ቀርቤ፣ እንደ ድልድይ ላቀራርባቸው ሞከርኩ፡፡ የሚሆን አይደለም፡፡ ያለበቂ ምክንያት፣ ላይታረቁ ተጣልተዋል፡፡ ለተጣላ ሰው ደግሞ፣ መካሰሻ ምክንያት አሽዋ ነው፡፡ መዳኘት ስራዬ ቢሆንም፣
ሰለቸኝ፡፡ ሁሉም ተበደልኩ ባይ ነው፡፡ ቀስ በቀስ ደስታዬ ተነነ፣ ሳቄና ጨዋታዬም ጠፋ፡፡ ብስጩና ነጭናጫ ሆንኩ፡፡ ወደ ስራዬ መሄድ ይሰለቸኝና ይጨንቀኝ ጀመረ። ስራተኛውና ድርጅቱ አንገሸገሹኝ፡፡ ካሁን በኋላ ስራ በፍፁም አለቅም ብዬ የገባሁትን ቃል መጠበቅ አቃተኝ፡፡ ሌላ ስራ እንኳን ሳላገኝ እንደዘበት መልቀቂያ አስገብቼ ጠፋሁ፡፡ ለአመት ተንከራተትቼ አዲስ ስራ አገኘሁ፡፡ አሁንም፣ እንደገና አይለምደኝም ብዬ
ስራ ልጀምር ነው፡፡
#እንደገና
“..ቋ..ቋ...ቋ...” ከአለቃዬ ቢሮ እንደወጣሁ፣ ኮሪደሩ ላይ፣ የሂል
ጫማ ድምፅ ተቀበለኝ፡፡ ድምፁን ወደሰማሁበት ቀና ብዬ ተመለከትኩ።
ፈዘዝ ያለ ቢጫ ቦዲ፣ በጥቁር ጨርቅ ሱሪ፣ የሚያምር የሰውነት ቅርፅ፣በረጅም ሂል ጫማ የተጫማች ልጅ ወደኔ አቅጣጫ እየመጣች ነው።ከአለቃዬ ቢሮ፣ የኔ ቢሮ ሩቅ ሚባል አይደለም፡፡ የጎረምሳ ነገር ልጅቷን በቅርበት ሳላያት ወደቢሮዬ መግባት አልፈለኩም፡፡ እንድትደርስብኝ እንደ ኤሊ ተጎተትኩ፡፡ አልተሳካም! ቢሮዬ በር ደረስኩ፡፡ ይሄኔ የሚመጣው
ሰው ማልፈልገው ሆኖ እንዳላየ ለመግባት ብጣደፍኮ ኖሮ.....። መጠበቅ
አለብኝ፡፡ ከአለቃዬ የተቀበልኩትን ወረቀት፣ የቢሮዬ በር ላይ ቆሜ
ማንበብ ጀመርኩ፡፡
ሄይ! አዲሱ ስታፋችን?” እጇን ዘረጋችልኝ..
“አዎ! ያቤዝ እባላለሁ፡፡” እጇን ጨብጬ ከላይ እስከታች በዐይኔ እየዳበስኳት፡፡
“ማሂ ቆንጆ እባላለሁ፡፡”
“እመሰክራለሁ! በጣም ቆንጆ ነሽ!፡፡”
ኪ.ኪ...ኪ...፣ አመሰግናለሁ፡፡ እንኳን ደህና መጣህ፡፡
በስርዓት አቀባበል እናደርጋለን፡፡” ብላ፣ የቆምኩበት ትታኝ፣ ወደ አለቃዬ
ቢሮ መሄድ ጀመረች፡፡
“አመሰግናለሁ!” እያልኩ፣ የጀርባ ውበቷን ለማረጋገጥ ካንገቴ ዞሬ በዐይኔ ተከተልኳት፡፡ ትንሽ እንደተራመደች እያየኋት እንደሆነ ለማረጋገጥ ይመስል፣ ድንገት ዞር ስትል ዐይን ለዐይን ተጋጨን፡፡ ወደ ቢሮዬ ተስፈንጥሬ ገባሁ፡፡ ሃሳቤ ግን ተከትሏት ሄዷል፡፡ ውበቷ ሙጫ ነው፣ ተጣብቆ የሚቀር፡፡ ማራኪ ነች፡፡ በዛ ላይ በደንብ ተኳኩላለች።ቢሆንም፣ ሲፈጥራትም ልቅም ያለች ቆንጆ ነች፡፡ ሃም...፣ ጥሩ ጥቅማ ጥቅም ያለው አሪፍ መስሪያ ቤት ነው የገባሁት፡፡ ይሄንን ቢነግሩኝ ኖሮ፣መች ደሞዙን እንደዛ እጨቃጨቃቸው ነበር፡፡ ምን ክፍል ይሆን
ምትሰራው...?”
ቢሮዬን ዝም ብዬ ተመለከትኩት፡፡ የሰለቸው የወንደ ላጤ ቤት መስሎ ተዝረክርኳል፡፡ እዚህ ቢሮ ውስጥ በቀን ስምንት ሰዓት መቆየት በራሱ ያደክማል፡፡ የጠረጴዛና ወንበሮቹ አቀማመጥ በዘፈቀደ ነው።ማስተካከል ጀመርኩ፡፡ ለስራ በሚመቸኝና ቢሮው የተሻለ እይታ
እስኪኖረው መላልሼ አዟዟርኳቸው፡፡ ማልፈልጋቸውን ወረቀቶች አስወገድኩ፤ ያስፈልጋሉ ምላቸውን፣ በየዘርፍ በየዘርፍ አድርጌ ፋይል ውስጥ አስቀመጥኳቸው፡፡ ስሰራ ሃሳቤ እንዲሰረቅ አልፈልግም፡፡ ቢሮ ውስጥ ያሉ ኮተቶችና ምስቅልቅሎች ሃሳብን ያናጥባሉ። በነፃነትና በትኩረት ስራዬን ለመስራት፣ በምችለው መጠን ቢሮዬን ስርዓት ያለውና ነፃ አደረኩት፡፡ ይህ በቀደሙት መስሪያ ቤቶቼም የምከውነው የመጀመሪያ ቀን ተግባሬ ነው፡፡ ጎንበስ ቀና ያልኩበት፣ እቃዎቹን
የጎተትኩበት ድካም ተሰማኝ፡፡ እርጅና ሊመጣ ነው፡፡ ትንፋሽ ለመውሰድ
ወንበር ላይ አረፍ አልኩ፡፡ ሰዓቴን ስመለከት የሻይ ሰዓት ደርሷል።
ሻይ በኋላ የቀረውን አስተካክለዋለሁ ብዬ እያሰብኩ፤
“ጤና ይስጥልኝ!...” ብለው አለቃዬ ወደ ቢሮዬ ገቡ። እጄን ጨብጠው ሰላምታ ተለዋወጥን፡፡ አለቃዬ መልከ መልካም፣ እድሜያቸው ጎልማሳነትን የዘለለ ይመስላሉ፡፡
“እንኳን ደህና መጡ!”
“ደግሞ ከመቼው ቢሮውን እንዲህ አሳመርከው...?፣ ይሄ ቢሮ እንዲህ ያምር ነበር እንዴ...?” በፈገግታ ጥርሳቸውን ፈልቀቅ አድርገው፡፡
“እንዲመቸኝ ትንሽ ነው የነካካሁት፡፡”
“ሌላ ቢሮ አስመስለህ አሳምረከዋል እንጂ፡፡ አይ ወጣት! መቼም ውበት ትወዳላችሁ! በል ና አሁን ቡና ልጋብዝህ፤ በዛውም ስታፎቻችንን ላስተዋውቅህ፤” ብለውኝ ከቢሮዬ ወጡ፡፡
“እሺ!” ብዬ ቢሮዬን ቆልፌ ተከተላኳቸው፡፡
ካፍቴሪያ ስንደርስ፣ ክብ ሰርተው እየተንጫጩ ሻይ ቡና የሚጠጡ ሰዎች ጋር ወስደው ቀላቀሉኝ፡፡ እየጮሁ ያወራሉ፤ እየጮሁ ይሳሳቃሉ፡፡ ይህ የግቢው አውራ ቡድን እንደሆነ ሁኔታቸው ይናገራል፡፡እየተሸቀዳደሙ ያወራሉ፤ ከፍ አድርገው ይስቃሉ፤ ያሽካካሉ፤ ሌላ ሰው
ይሰማናል፣ እንረብሻለን፣ ምን ይሉናል ሚሉት ነገሮች ሚያሳስቧቸው አይመስሉም፡፡
“ጎበዝ አዲሱ አድሚናችንን ትተዋወቁት ዘንድ ይዤው መጥቻለሁ፡፡ ያቤዝ ይባላል፡፡ እናንተ ደግሞ እራሳችሁን አስተዋውቁት፧”ብለው ወንበር ስበው ተቀመጡ፡፡ ጫጫታቸውን አቁመው፣ ፀጥ ብለው ካዳመጡ በኋላ፣ በአንድ ላይ፣ “እንኳን ደህና መጣህ! ዌል ካም!›› ብለው አልጎመጎሙ:: አራት ሴትና ሶስት ወንድ ናቸው፡፡ ሴቶቹ ወጣትና ቆነጃጅት ሲሆኑ፣ ወንዶቹ በእድሜ ከፍ ከፍ ያሉና፣ ሙሉ ሰውነት ያልደረሱ ጎልማሶች ናቸው።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ(MD)
1.ቅድመ ታሪክ
ከአንድ ዓመት ስራ መፍታት በኋላ፣ እንደገና ስራ ልጀምር ነው። በማኔጅመንት ሁለተኛ ድግሪና ከአስር ዓመት በላይ የስራ ልምድ አለኝ። ያለ ስራ በቆየሁበት ግዜ፣ ያጠራቀምኩትን ገንዘብ ጨርሼ
ንብረቶቼን ሸጥኩ፡፡ አሁን መኪናዬን ለመሸጥ በማሰብ ላይ ሳለሁ ስራ
አገኘሁ፡፡ ከባድ ግዜ ነበር፡፡ ንብረት ከማጣት በተጨማሪ፣ የስነ ልቦና ጉዳቱ ይሄ ነው ሚባል አይደለም፡፡ በራሴ ያለኝ መተማመን በከፍተኛ ደረጃ አሽቆልቁሏል፡፡ ከዚህ በፊትም፣ በተመሳሳይ ስራ ለቅቄ እስክፀፀት
ተቸግሬ አውቃለሁ፡፡ ሁለተኛ ብዬ ለራሴ ቃል ገብቼ ነበር፡፡ ቃሌን መጠበቅ አቅቶኝ፣ ይኸው ለአመት ተንከራተትኩ፡፡
የመጨረሻው ድርጅቴ በጣም ጥሩ ክፍያን ይከፍለኝ ነበር፡፡በተጨማሪም፣ ለሙያዬ እድገት የሚረዱኝ የተለያዩ የስልጠና እድሎችን በሃገር ውስጥና በውጪ ሃገራት ያመቻችልኝ ነበር፡፡ በጣም ደስተኛ ሆኜ ነበር፡፡ ብዙ እንደምቆይበት ተሰምቶኝ ነበር፡፡ ከተወሰነ ግዜ በኋላ ግን፣ሰራተኛው የተከፋፈለና በየቀኑ የሚካሰስ እንደሆነ እየተሰማኝ መጣ፡፡እኔ ደግሞ እንደ አስተዳደር ስራዬ መዳኘት ነው፤ አንዱን በዳይ፣አንዱን ተበዳይ አድርጎ መፍረድ፡፡ እኔ ደግሞ፣ ከመፍረድና ከመቅጣት ይልቅ፣ ችግሩን በማስታረቅ መፍታት የተሻለ መስሎ ተሰማኝ፡፡ እንደዛ ሞከርኩ። አይሳካም፡፡ ጭራሽ ወደኋላ አምስት፣ አስር ዓመት
ተመልሰው፣ “እርሱ/እርሷ፣ ባለፈውም እንዲህ በድሎኝ/ላኝ፣” እያሉ ሌላ
የክስ ቱባ ይተረትራሉ።
ጓደኛ ሆኜ ቀርቤያቸው፣ መሰረታዊ የፀባቸውን መንስኤ ለማወቅ
ሞከርኩ፡፡ ከአሉባልታ የዘለለ፣ ይሄ ነው የሚባል የከፋ ነገር የላቸዉም፡፡ክሶቻቸው ከጥርጣሬና፣ ሳይቀድመኝ ልቅደመው ከማለት የሚመነጩ ናቸው። እኩል ቀርቤ፣ እንደ ድልድይ ላቀራርባቸው ሞከርኩ፡፡ የሚሆን አይደለም፡፡ ያለበቂ ምክንያት፣ ላይታረቁ ተጣልተዋል፡፡ ለተጣላ ሰው ደግሞ፣ መካሰሻ ምክንያት አሽዋ ነው፡፡ መዳኘት ስራዬ ቢሆንም፣
ሰለቸኝ፡፡ ሁሉም ተበደልኩ ባይ ነው፡፡ ቀስ በቀስ ደስታዬ ተነነ፣ ሳቄና ጨዋታዬም ጠፋ፡፡ ብስጩና ነጭናጫ ሆንኩ፡፡ ወደ ስራዬ መሄድ ይሰለቸኝና ይጨንቀኝ ጀመረ። ስራተኛውና ድርጅቱ አንገሸገሹኝ፡፡ ካሁን በኋላ ስራ በፍፁም አለቅም ብዬ የገባሁትን ቃል መጠበቅ አቃተኝ፡፡ ሌላ ስራ እንኳን ሳላገኝ እንደዘበት መልቀቂያ አስገብቼ ጠፋሁ፡፡ ለአመት ተንከራተትቼ አዲስ ስራ አገኘሁ፡፡ አሁንም፣ እንደገና አይለምደኝም ብዬ
ስራ ልጀምር ነው፡፡
#እንደገና
“..ቋ..ቋ...ቋ...” ከአለቃዬ ቢሮ እንደወጣሁ፣ ኮሪደሩ ላይ፣ የሂል
ጫማ ድምፅ ተቀበለኝ፡፡ ድምፁን ወደሰማሁበት ቀና ብዬ ተመለከትኩ።
ፈዘዝ ያለ ቢጫ ቦዲ፣ በጥቁር ጨርቅ ሱሪ፣ የሚያምር የሰውነት ቅርፅ፣በረጅም ሂል ጫማ የተጫማች ልጅ ወደኔ አቅጣጫ እየመጣች ነው።ከአለቃዬ ቢሮ፣ የኔ ቢሮ ሩቅ ሚባል አይደለም፡፡ የጎረምሳ ነገር ልጅቷን በቅርበት ሳላያት ወደቢሮዬ መግባት አልፈለኩም፡፡ እንድትደርስብኝ እንደ ኤሊ ተጎተትኩ፡፡ አልተሳካም! ቢሮዬ በር ደረስኩ፡፡ ይሄኔ የሚመጣው
ሰው ማልፈልገው ሆኖ እንዳላየ ለመግባት ብጣደፍኮ ኖሮ.....። መጠበቅ
አለብኝ፡፡ ከአለቃዬ የተቀበልኩትን ወረቀት፣ የቢሮዬ በር ላይ ቆሜ
ማንበብ ጀመርኩ፡፡
ሄይ! አዲሱ ስታፋችን?” እጇን ዘረጋችልኝ..
“አዎ! ያቤዝ እባላለሁ፡፡” እጇን ጨብጬ ከላይ እስከታች በዐይኔ እየዳበስኳት፡፡
“ማሂ ቆንጆ እባላለሁ፡፡”
“እመሰክራለሁ! በጣም ቆንጆ ነሽ!፡፡”
ኪ.ኪ...ኪ...፣ አመሰግናለሁ፡፡ እንኳን ደህና መጣህ፡፡
በስርዓት አቀባበል እናደርጋለን፡፡” ብላ፣ የቆምኩበት ትታኝ፣ ወደ አለቃዬ
ቢሮ መሄድ ጀመረች፡፡
“አመሰግናለሁ!” እያልኩ፣ የጀርባ ውበቷን ለማረጋገጥ ካንገቴ ዞሬ በዐይኔ ተከተልኳት፡፡ ትንሽ እንደተራመደች እያየኋት እንደሆነ ለማረጋገጥ ይመስል፣ ድንገት ዞር ስትል ዐይን ለዐይን ተጋጨን፡፡ ወደ ቢሮዬ ተስፈንጥሬ ገባሁ፡፡ ሃሳቤ ግን ተከትሏት ሄዷል፡፡ ውበቷ ሙጫ ነው፣ ተጣብቆ የሚቀር፡፡ ማራኪ ነች፡፡ በዛ ላይ በደንብ ተኳኩላለች።ቢሆንም፣ ሲፈጥራትም ልቅም ያለች ቆንጆ ነች፡፡ ሃም...፣ ጥሩ ጥቅማ ጥቅም ያለው አሪፍ መስሪያ ቤት ነው የገባሁት፡፡ ይሄንን ቢነግሩኝ ኖሮ፣መች ደሞዙን እንደዛ እጨቃጨቃቸው ነበር፡፡ ምን ክፍል ይሆን
ምትሰራው...?”
ቢሮዬን ዝም ብዬ ተመለከትኩት፡፡ የሰለቸው የወንደ ላጤ ቤት መስሎ ተዝረክርኳል፡፡ እዚህ ቢሮ ውስጥ በቀን ስምንት ሰዓት መቆየት በራሱ ያደክማል፡፡ የጠረጴዛና ወንበሮቹ አቀማመጥ በዘፈቀደ ነው።ማስተካከል ጀመርኩ፡፡ ለስራ በሚመቸኝና ቢሮው የተሻለ እይታ
እስኪኖረው መላልሼ አዟዟርኳቸው፡፡ ማልፈልጋቸውን ወረቀቶች አስወገድኩ፤ ያስፈልጋሉ ምላቸውን፣ በየዘርፍ በየዘርፍ አድርጌ ፋይል ውስጥ አስቀመጥኳቸው፡፡ ስሰራ ሃሳቤ እንዲሰረቅ አልፈልግም፡፡ ቢሮ ውስጥ ያሉ ኮተቶችና ምስቅልቅሎች ሃሳብን ያናጥባሉ። በነፃነትና በትኩረት ስራዬን ለመስራት፣ በምችለው መጠን ቢሮዬን ስርዓት ያለውና ነፃ አደረኩት፡፡ ይህ በቀደሙት መስሪያ ቤቶቼም የምከውነው የመጀመሪያ ቀን ተግባሬ ነው፡፡ ጎንበስ ቀና ያልኩበት፣ እቃዎቹን
የጎተትኩበት ድካም ተሰማኝ፡፡ እርጅና ሊመጣ ነው፡፡ ትንፋሽ ለመውሰድ
ወንበር ላይ አረፍ አልኩ፡፡ ሰዓቴን ስመለከት የሻይ ሰዓት ደርሷል።
ሻይ በኋላ የቀረውን አስተካክለዋለሁ ብዬ እያሰብኩ፤
“ጤና ይስጥልኝ!...” ብለው አለቃዬ ወደ ቢሮዬ ገቡ። እጄን ጨብጠው ሰላምታ ተለዋወጥን፡፡ አለቃዬ መልከ መልካም፣ እድሜያቸው ጎልማሳነትን የዘለለ ይመስላሉ፡፡
“እንኳን ደህና መጡ!”
“ደግሞ ከመቼው ቢሮውን እንዲህ አሳመርከው...?፣ ይሄ ቢሮ እንዲህ ያምር ነበር እንዴ...?” በፈገግታ ጥርሳቸውን ፈልቀቅ አድርገው፡፡
“እንዲመቸኝ ትንሽ ነው የነካካሁት፡፡”
“ሌላ ቢሮ አስመስለህ አሳምረከዋል እንጂ፡፡ አይ ወጣት! መቼም ውበት ትወዳላችሁ! በል ና አሁን ቡና ልጋብዝህ፤ በዛውም ስታፎቻችንን ላስተዋውቅህ፤” ብለውኝ ከቢሮዬ ወጡ፡፡
“እሺ!” ብዬ ቢሮዬን ቆልፌ ተከተላኳቸው፡፡
ካፍቴሪያ ስንደርስ፣ ክብ ሰርተው እየተንጫጩ ሻይ ቡና የሚጠጡ ሰዎች ጋር ወስደው ቀላቀሉኝ፡፡ እየጮሁ ያወራሉ፤ እየጮሁ ይሳሳቃሉ፡፡ ይህ የግቢው አውራ ቡድን እንደሆነ ሁኔታቸው ይናገራል፡፡እየተሸቀዳደሙ ያወራሉ፤ ከፍ አድርገው ይስቃሉ፤ ያሽካካሉ፤ ሌላ ሰው
ይሰማናል፣ እንረብሻለን፣ ምን ይሉናል ሚሉት ነገሮች ሚያሳስቧቸው አይመስሉም፡፡
“ጎበዝ አዲሱ አድሚናችንን ትተዋወቁት ዘንድ ይዤው መጥቻለሁ፡፡ ያቤዝ ይባላል፡፡ እናንተ ደግሞ እራሳችሁን አስተዋውቁት፧”ብለው ወንበር ስበው ተቀመጡ፡፡ ጫጫታቸውን አቁመው፣ ፀጥ ብለው ካዳመጡ በኋላ፣ በአንድ ላይ፣ “እንኳን ደህና መጣህ! ዌል ካም!›› ብለው አልጎመጎሙ:: አራት ሴትና ሶስት ወንድ ናቸው፡፡ ሴቶቹ ወጣትና ቆነጃጅት ሲሆኑ፣ ወንዶቹ በእድሜ ከፍ ከፍ ያሉና፣ ሙሉ ሰውነት ያልደረሱ ጎልማሶች ናቸው።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍3👏2
አበባ:
#እውነት_እናውራ_ካልሽ
“በይ” ስልሽ .. “ወዶኝ ነው”
“ተይ” ስልሽ .. “ቀንቶ ነው!”
ባልሽበት አንደበት፥
ዝም ስል .. “ንቆኝ ነው!”
ብትይ ምናለበት ?!
🔘በዮሐንስ🔘
#እውነት_እናውራ_ካልሽ
“በይ” ስልሽ .. “ወዶኝ ነው”
“ተይ” ስልሽ .. “ቀንቶ ነው!”
ባልሽበት አንደበት፥
ዝም ስል .. “ንቆኝ ነው!”
ብትይ ምናለበት ?!
🔘በዮሐንስ🔘
#የአፍሪካ_አናብስት
አምላክ! ት......ልቅ ነገር ለአፍሪካ አድሏታል
አንበሳ 'ሚበላ አንበሳ ሰጥቷታል፡፡
አንት የአፍሪካ መንጋ - አንት የአፍሪካ አንበሳ
ነፍጠኛ ቀርቦሃል በል ነፍጥህን አንሳ፡፡
ካደክበት ቀየ ፣ ካደክበት መንደር
ማዕድን ሲወጣ ፣ መሬትህ ሲቆፈር
ምንድን ነው ማፈግፈግ!?፣ ምንድን ነው ማቀርቀር!?
አይዞህ የኛ አንበሳ!- አይዞህ የኛ ጀግና!
ብዕርህን ጥለህ ነፍጥህን አንሳና፣
እጫካህ ግባና፣
ጨፍጭፍ ወንድምህን፤
ጨፍጭፍ እህትህን፤
ጨፍጭፍ አባትህን፤
ጨፍጭፍ እናትህን፤
ጨፍጭፍ!
ጨፍጭፍ!
ጨፍጭፍ!......
ጨፍጭፋቸው ሁሉን!
ኖረው ካላኮሩን
ዛፍ ይብቀልባቸው አፈር ይሁኑ አሁን፡፡
ተነስ ያዝ ቦንብህን
ይብሱን ጎትታት ጎታታ አገርህን፡፡
ወዲያ የምን ልማት?
የምን ኢንዱስትሪ? ፣ የምን የአገር እድገት?
የጓሮህ ማዕድን
ተቆፍሮ ወጥቶ አገር ከሚያድግበት
አንተ ሽጠውና መሳሪያ ግዛበት፤
መሳሪያ ግዛና ወገን ግደልበት፤
ወገን ግደልና ለስልጣን ተሯሯጥ፤
ያልለፉበት ዳቦ ድሮም ቢሆን አይጣፍጥ፡፡
አንት የአፍሪካ ጀግና አንት የአፍሪካ አንበሳ
ነፍጠኛ ቀርቦሃል -በል ነፍጥህን አንሳ፡፡
ለወንበር ሲሮጡ ለወንበር ተነሳ
ለስልጣን ከቸኮልክ ለሰው ነብስ አትሳሳ፡፡
አየህ አሜሪካን!?
አየህ እነ አውሮጳን!?
ከንቱ ሲጃጃሉ፤
‹ስልጣን በህዝብ እንጂ-
በነፍጥ አናገኝም!›
ብለው ሲማማሉ፡፡
አየህ እነ ህንድን!?
አየህ እነ ቻይናን!?
አየህ ያገር ፈሪ!?
ነፍጣቸውን ጥለው ሲያስፋፉ እንዱስትሪ፡፡
እንትፍ!
ወንድ አሰዳቢዎች ልፍስፍስ እንደ እበት
እነዚህን ነበር
በአንድ ቦምብ ጨፍልቆ ከአለም ማሰናበት፡፡
ቢሆንም እርሳቸው ምንም አይሰሩልህ
ፈንጅ መትረየስ ግን ተቀበል ሲሰጡህ፡፡
🔘በሙሉቀን🔘
አምላክ! ት......ልቅ ነገር ለአፍሪካ አድሏታል
አንበሳ 'ሚበላ አንበሳ ሰጥቷታል፡፡
አንት የአፍሪካ መንጋ - አንት የአፍሪካ አንበሳ
ነፍጠኛ ቀርቦሃል በል ነፍጥህን አንሳ፡፡
ካደክበት ቀየ ፣ ካደክበት መንደር
ማዕድን ሲወጣ ፣ መሬትህ ሲቆፈር
ምንድን ነው ማፈግፈግ!?፣ ምንድን ነው ማቀርቀር!?
አይዞህ የኛ አንበሳ!- አይዞህ የኛ ጀግና!
ብዕርህን ጥለህ ነፍጥህን አንሳና፣
እጫካህ ግባና፣
ጨፍጭፍ ወንድምህን፤
ጨፍጭፍ እህትህን፤
ጨፍጭፍ አባትህን፤
ጨፍጭፍ እናትህን፤
ጨፍጭፍ!
ጨፍጭፍ!
ጨፍጭፍ!......
ጨፍጭፋቸው ሁሉን!
ኖረው ካላኮሩን
ዛፍ ይብቀልባቸው አፈር ይሁኑ አሁን፡፡
ተነስ ያዝ ቦንብህን
ይብሱን ጎትታት ጎታታ አገርህን፡፡
ወዲያ የምን ልማት?
የምን ኢንዱስትሪ? ፣ የምን የአገር እድገት?
የጓሮህ ማዕድን
ተቆፍሮ ወጥቶ አገር ከሚያድግበት
አንተ ሽጠውና መሳሪያ ግዛበት፤
መሳሪያ ግዛና ወገን ግደልበት፤
ወገን ግደልና ለስልጣን ተሯሯጥ፤
ያልለፉበት ዳቦ ድሮም ቢሆን አይጣፍጥ፡፡
አንት የአፍሪካ ጀግና አንት የአፍሪካ አንበሳ
ነፍጠኛ ቀርቦሃል -በል ነፍጥህን አንሳ፡፡
ለወንበር ሲሮጡ ለወንበር ተነሳ
ለስልጣን ከቸኮልክ ለሰው ነብስ አትሳሳ፡፡
አየህ አሜሪካን!?
አየህ እነ አውሮጳን!?
ከንቱ ሲጃጃሉ፤
‹ስልጣን በህዝብ እንጂ-
በነፍጥ አናገኝም!›
ብለው ሲማማሉ፡፡
አየህ እነ ህንድን!?
አየህ እነ ቻይናን!?
አየህ ያገር ፈሪ!?
ነፍጣቸውን ጥለው ሲያስፋፉ እንዱስትሪ፡፡
እንትፍ!
ወንድ አሰዳቢዎች ልፍስፍስ እንደ እበት
እነዚህን ነበር
በአንድ ቦምብ ጨፍልቆ ከአለም ማሰናበት፡፡
ቢሆንም እርሳቸው ምንም አይሰሩልህ
ፈንጅ መትረየስ ግን ተቀበል ሲሰጡህ፡፡
🔘በሙሉቀን🔘
#የታካሚው_ማስታወሻ
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ(MD)
ከሁሉም ወንዶች በእድሜ ወጣት እንደሆንኩ ተስማኝ፡፡ እየዞርኩ :
እየጨበጥኩ መተዋወቅ ጀመረኩ...::
“ኤፍሬም፣ እንኳን ደህና መጣህ!”
“ማሂ ቆንጆ፣ ቅድም ተዋውቀናል፡፡”
“ሳሚ፣ እንኳን ደህና መጣህ!”
“ቤቲ፣ እንኳን ደህና መጣህ!”
“ግርማ፣ እንኳን ደህና መጣህ!”
ፌቨን፣ እንኳን ደህና መጣህ...?”
“ሜሪ፣ እንኳን ደህና መጣህ...?”
ሁሉም በፈግታና አክብሮት በተሞላ ሁኔታ ሰላምታ ሰጥተው ተዋወቁኝ፡፡ ሳምሶን ከጎኑ እንድቀመጥ ወንበር ስቦ ጋበዘኝ፡፡ አስተናጋጇ :ስትመጣ፣ እንደኔ ጠቆር ያለ ማኪያቶ ብዬ አዘዝኩ፡ ሴቶቹ ዞር ብለው
የፊት ቀለሜን ተመለከቱ፡፡ እኔም እንደዛ ብዬ ያዘዝኩት ይሄን ፈልጌ ነበር፡፡ ወደ ጫጫታቸው ተመለሱ፡፡ እኩል እየጮሁ ያወራሉ። ማንን ማዳመጥ እንዳለብኝ ግራ እስኪገባኝ፣ ይሽቀዳደማሉ፤ ይበሻሸቃሉ፣ በጣም ይስቃሉ፤ ፊታቸው ላይ የሚነበበው ደስታና እርካታ ያስቀናል። ማሂ ቆንጆ በጣም ታወራለች። ትስቃለች፡፡ በየመሃሉ በዐይኗ ተጫወት
ትለኛለች፡፡ አለቃዬ እየተሳሳቁ ትንሽ ከተጫወቱ በኋላ፣ “በሉ አስለምዱት!” ብለው ተነስተው ወደ ቢሮ ሄዱ። አሪፍ መስሪያ ቤት እንደገባሁ ሁለት ማስረጃዎች አገኘሁ፤ ደስ የሚል አለቃና ፍቅርና እርካታ የተሞሉ ሰራተኞች፡፡ አለቃማ እንደዚህ ነው፤ ለሰራተኞቹ ያለው
ቀረቤታና አክብሮት ሚያስቀና ነው፡፡ በውስጤ 'ዋ ው! ፀዴ መስሪያ ቤት
ነው የገባሁት፤' አልኩኝ፡፡ ከቀድሞው መስሪያ ቤቴ ጋር አነፃፅሬ ውስጤ
በደስታ ሞቀ። እዚህ ፍቅራቸው የሚያስቀና፣ በመስሪያ ቤታቸው ደስተኛ
የሆኑ፣ በመልክ ተመርጠው የተቀጠሩ የሚመስሉ፣ የውብ ሴቶች ጥርቅም፡፡ ያወራሉ፤ ይስቃሉ፣ በየመሃሉ “ተጫወት!” ይሉኛል፡፡ ቀስ ብዬ የሴቶቹን የግራ እጆቻቸውን ተመለከትኩ፡፡ ጣቶቻቸው ላይ ቀለበት የለም፡፡ 'ያብ ከእነዚህ ውስጥ ሚስት ካላገኘህ፣ መቼም አታገኝም፡፡' ብዬ
ወደ ውስጤ አንሾካሾኩ፡፡
ከሻይ በኋላ ወደ ቢሮ ስመለስ፣ ግቢውን በደንብ ተመለከትኩት፡፡ ወደ ፋብሪካው፣ ወደ እስቶር፣ ወደ ዋናው ቢሮ የሚወስዱትን መንገዶች በሚገባ ዲዛይን ተደርገው የተሰሩ ናቸው፡፡ በባለሙያ የተያዘ ሚመስለው አረንጓዴ ቦታ በፈኩ አበቦች ደምቋል፡፡ እኮርነር ላይ በግማሽ ጎጆ ቅርፅ የተሰራው ነፋሻማ የሰራተኛ ክበብ፣ መሀል ላይ ለግቢው ሞገስ እንዲሆን ተደርጎ የተሰራው፣ ነጨ ባለ አንድ ፎቅ የአስተዳደር ህንፃ የመዝናኛ
ቦታ ይመስላል፡፡ ቢሮዬ እንደተመለስኩ፣ የቀረኝን እንደምፈልገው አስተካክዬ ጨረስኩ፡፡ የተሰጠኝን ኮምፒውተር ከፍቼ፣ ስለመስሪያ ቤቱ የተሻለ ምስል ይስጡኛል ያልኳቸውን መረጃዎች ለማግኝት ፋይሎች እየከፈትኩ በማንበብ ተጠመድኩ፡፡ ድርጅቱ ትልቅ ራዕይ እንዳለው ተረዳሁ፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተፎካካሪ የመሆንና በሀገራችን ላሉ .
ተመሳሳይ የጨርቃ ጨርቅ ድርጅቶችም የልህቀት ማዕከል መሆን ራዕዩ አድርጎ አስቀምጧል፡፡ ለዚህ ደግሞ ታታሪና ውጤታማ የሆኑ ሰራተኞችን ዋንኛ ግብአት ብቻ ሳይሆኑ፣ ምሰሶና ማገር ናቸው ብሎ ይተነትናል። ሰራተኞቹ ለምን እንደዛ ደስተኛ እንደሆኑ አሁን
ተገለፀልኝ፡፡ አስር ሰዓት ተኩል ሲሆን፣ እንደ አዲስ ጎጆ ወጪ፣ ሳይመሽ
አንድ አንድ ያልገዛኋቸውን የቤት እቃዎች ለመግዛት ቀድሜ ወጣሁ፡፡እቃዎቹን ገዛዝቼ፣ እራት በልቼ ወደ ቤት ገባሁ፡፡ ደስ ሚል ቀን ነበር፡፡ደክሞኝ ስለነበር እንቅልፍ ቶሎ ወሰደኝ፡፡
።።።።።
ስራ ከጀመርኩ ልክ አንድ ወር ሞላኝ፡፡ ስራውና የስራ ከባቢዬ ተስማምቶኛል፡፡ የስራ ፍላጎቴና ተነሳሽነቴ ተመልሶ ከፍ ብሏል፡፡ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ስራዬን በፍጥነት ለማወቅና ለመረዳት
ችያለሁ፡፡ የተለያዩ ፋይሎችን፣ ደብዳቤዎችን አገላብጬ አነበብኩ።
ከሰዎችና ከሰራተኞች ጋር የመተዋወቅና የመቀራረብ ፍላጎቴም ከፍ ብሎ፣ ሰራተኞችን በየክፍሉ እየዞርኩ እየተዋወኩ አናገርኩ፡፡ የስራ ቅልጥፍናዬ ከሰራተኛው ጋር ያለኝ መግባባትና የስራ ተነሳሽነቴ
በአለቃዬም ሆነ በሰራተኛው ከጠበኩት ፍጥነት በላይ ታማኝነትና ከበሬታን አስገኘልኝ፡፡ በየቀኑ ከማከናውናቸው የዕለት ተዕለት ስራዎች በተጨማሪ፣ ድርጅቱ ያስቀመጠውን ራዕይ ለማሳካት፣ ይጠቅማል ያልኳቸውን ለመስራት እሞክራለሁ፡፡
ሰራተኛውንም የድርጅቱን ራዕይ ተገንዝቦ፣ በዛው መጠን እንዲተጋ አነቃቃለሁ፤ እመክራለሁ፡፡ከስኞ እስከ ቅዳሜ እንሰራለን፡፡ ቅዳሜ ግማሽ ቀን ስለሆነ፣
ከነሳሚ ጋር ተያይዘን እንወጣለን፤ ምሳ በልተን እየጠጣን መጫወት ልምድ ሆኗል፡፡ አለቃዬ አንዳንዴ አብረውን ወጥተው ይጋብዙናል፡፡ከቆነጃጅቶች አንዷን ለማጥመድ፣ በደፈናው ሁሉም ላይ መረቤን ዘርግቻለሁ፡፡ ወጣትነቴንና ወንደላጤነቴን እንደ የመጫወቻ ካርድ
አድርጌ እየተጠቀምኩበት ነው፡፡ አሁን በስራዬም በህይወቴም ደስተኛ
ሆኛለሁ፡፡ ዛሬ ሰኞ ነው፡፡ ሁሌ ሰኞ እንደምለብሰው፣ ሙሉ ሱፍ በከረባት
ለብሻለሁ፡፡ የመጀመሪያ ወርሃዊ የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ከእቅድ ጋር
እያነፃፀርኩ እየሰራሁ ነው፡፡
“መግባት ይቻላል...?” ማሂ ቆንጆ ነች፡፡
ሎርድ...!” ሳላስበው ከአፌ አመለጠኝ፡፡ ዛሬ ደግሞ ብሶባታል፡፡ጥቁር ቀሚስ፣ በጥቁር ሂል ጫማ አድርጋለች፡፡ ፀጉሯን ሂውማን ሄር በደንብ ተሰርታለች፡፡ ያልተሸፈኑት ታፋዎቿ ቀይ ፍም መስለው
ተቃቅፈዋል፡፡ እመሃል ግባ ግባ የሚል ስሜት ድንገት ነዘረኝ፡፡
“ምን አልከኝ ያቡ?" አለችኝ፣ ፈገግ ብላ፡፡
“መጠየቁስ ነው ያልኩሽ...”
“ሳይጠየቅማ አይገባም! ሌላ ሰው ቢኖርስ?” ፈገግ አለች፡፡
“ውይ ለካ እንደዛም አለ፡፡ ያለቃ ፀሃፊ መሆንኮ።”ሰምታኝ ይሆን? ተንተባተብኩ፡፡
“ይሄን ደግሞ ማን ነው የሰጠህ?”
“የቱን?” እንዳልገባኝ አብሪያት ዞሬ እያየሁ፡፡
“አበባውን ነዋ፡፡ በናትህ ማናት ያመጣችልህ? ኪ.ኪ.ኪ.”
“እንዴ...! ለምን ማናት አልሽኝ? ምን ማለት ፈልገሽ ነው?”
“ያው ሰሞኑን፣ የግቢውን ሴቶች አየር ስለተቆጣጠርከው፣ አንዷ
አምጥታልህ ይሆናል ብዬ ነዋ! ኪ.ኪ.ኪ...”
“አንቺ ደግሞ ትቀልጂያለሽ፡፡ እራሴ ነኝ ያመጣሁት፡፡ እንዳንቺ ያለች አበባ ምትመስል ፀሀፊ ባይመድቡልኝም፣ ቢሮዬን በአበባ ላሳምር ብዬ ነው፡፡”
“እረ ባክህ..! ኪ.ኪ.ኪ... እኔ ምልህ ያቡ፣ በናትህ ዛሬም ላስቸግርህ?”
“ምን ልታዘዝ? ደግሞ ላንቺ...”
“ማታ ስንወጣ ምሄድበት ነበረኝ፤ ታደርሰኛለህ? እንዲህ ለብሼ በታክሲ መሄድ...” ብላ ዝቅ ብላ ዳሌዋንና ጫማዋን በዐይኗ ጋበዘችኝ፡፡ዕይኖቿን ተከትዬ ቀያይ ታፋዎቿ መሃል ገባሁ፡፡
ድንገት የታፋዎቼ መሃል ሙቀት ሲጨምር፣ እመሃሉ እሳተ ሲለኮስ ተሰማኝ፡፡ ሳላስበው፣
“ግን ዛሬ ትንሽ አመሻለሁ፤” አልኩኝ፡፡
“እስከ ስንት ሰዐት?”
“እስከ አስራ ሁለት፣” ካፈርኩ አይመልሰኝ፡፡
“ችግር የለም እጠብቅሃለው።”
ካላስመሸሁሽ፣ እሺ እሽኝሻለሁ።”
ከማሂላ ጋር ተቀራርበናል፡፡ በፍጥነት ቤተሰብ አድርጋኛለች፡፡በተደጋጋሚ እንድሸኛት ጠይቃኝ፣ አድርሻታለሁ፡፡ ሻይ ቡናም፣ እራትም ጋብዤያታለሁ፡፡ እንድገባ በሯን እንደከፈተችልኝ ገብቶኛል፡፡ እንዳልገባኝ አልፈዋለሁ፡፡ ማታ ሸኝቼያት ስትወርድ በከፊል ከንፈሬን ስማኝ
ትወርዳለች፡፡ ምንም እንዳልተፈጠረ ደና እደሪ ብያት እሄዳለሁ።መጀመሪያ ቀን የደነገጠላት ልቤ ስትቀርበኝ ቀዝቀዝ አለ፡፡ ከእርሷ ይልቅ ወደ ሜሪ እንዳደላ ይሰማኛል፡፡ ከሜሪ ጋር ብዙ የመገናኘት እድል የለኝም፡፡ በአካል አንዴ ብቻ ነው አግኝቼ ሻይ ቡና ያልኳት፡፡ በስልክ
ግን ብዙ እናወራለን፡፡ ፍላጎት እንዳላት፣ ቢጫ መብራት አሳይታኛለች፡፡ ውስጤ ለሜሪ ስላደላ
፡
፡
#ክፍል_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ(MD)
ከሁሉም ወንዶች በእድሜ ወጣት እንደሆንኩ ተስማኝ፡፡ እየዞርኩ :
እየጨበጥኩ መተዋወቅ ጀመረኩ...::
“ኤፍሬም፣ እንኳን ደህና መጣህ!”
“ማሂ ቆንጆ፣ ቅድም ተዋውቀናል፡፡”
“ሳሚ፣ እንኳን ደህና መጣህ!”
“ቤቲ፣ እንኳን ደህና መጣህ!”
“ግርማ፣ እንኳን ደህና መጣህ!”
ፌቨን፣ እንኳን ደህና መጣህ...?”
“ሜሪ፣ እንኳን ደህና መጣህ...?”
ሁሉም በፈግታና አክብሮት በተሞላ ሁኔታ ሰላምታ ሰጥተው ተዋወቁኝ፡፡ ሳምሶን ከጎኑ እንድቀመጥ ወንበር ስቦ ጋበዘኝ፡፡ አስተናጋጇ :ስትመጣ፣ እንደኔ ጠቆር ያለ ማኪያቶ ብዬ አዘዝኩ፡ ሴቶቹ ዞር ብለው
የፊት ቀለሜን ተመለከቱ፡፡ እኔም እንደዛ ብዬ ያዘዝኩት ይሄን ፈልጌ ነበር፡፡ ወደ ጫጫታቸው ተመለሱ፡፡ እኩል እየጮሁ ያወራሉ። ማንን ማዳመጥ እንዳለብኝ ግራ እስኪገባኝ፣ ይሽቀዳደማሉ፤ ይበሻሸቃሉ፣ በጣም ይስቃሉ፤ ፊታቸው ላይ የሚነበበው ደስታና እርካታ ያስቀናል። ማሂ ቆንጆ በጣም ታወራለች። ትስቃለች፡፡ በየመሃሉ በዐይኗ ተጫወት
ትለኛለች፡፡ አለቃዬ እየተሳሳቁ ትንሽ ከተጫወቱ በኋላ፣ “በሉ አስለምዱት!” ብለው ተነስተው ወደ ቢሮ ሄዱ። አሪፍ መስሪያ ቤት እንደገባሁ ሁለት ማስረጃዎች አገኘሁ፤ ደስ የሚል አለቃና ፍቅርና እርካታ የተሞሉ ሰራተኞች፡፡ አለቃማ እንደዚህ ነው፤ ለሰራተኞቹ ያለው
ቀረቤታና አክብሮት ሚያስቀና ነው፡፡ በውስጤ 'ዋ ው! ፀዴ መስሪያ ቤት
ነው የገባሁት፤' አልኩኝ፡፡ ከቀድሞው መስሪያ ቤቴ ጋር አነፃፅሬ ውስጤ
በደስታ ሞቀ። እዚህ ፍቅራቸው የሚያስቀና፣ በመስሪያ ቤታቸው ደስተኛ
የሆኑ፣ በመልክ ተመርጠው የተቀጠሩ የሚመስሉ፣ የውብ ሴቶች ጥርቅም፡፡ ያወራሉ፤ ይስቃሉ፣ በየመሃሉ “ተጫወት!” ይሉኛል፡፡ ቀስ ብዬ የሴቶቹን የግራ እጆቻቸውን ተመለከትኩ፡፡ ጣቶቻቸው ላይ ቀለበት የለም፡፡ 'ያብ ከእነዚህ ውስጥ ሚስት ካላገኘህ፣ መቼም አታገኝም፡፡' ብዬ
ወደ ውስጤ አንሾካሾኩ፡፡
ከሻይ በኋላ ወደ ቢሮ ስመለስ፣ ግቢውን በደንብ ተመለከትኩት፡፡ ወደ ፋብሪካው፣ ወደ እስቶር፣ ወደ ዋናው ቢሮ የሚወስዱትን መንገዶች በሚገባ ዲዛይን ተደርገው የተሰሩ ናቸው፡፡ በባለሙያ የተያዘ ሚመስለው አረንጓዴ ቦታ በፈኩ አበቦች ደምቋል፡፡ እኮርነር ላይ በግማሽ ጎጆ ቅርፅ የተሰራው ነፋሻማ የሰራተኛ ክበብ፣ መሀል ላይ ለግቢው ሞገስ እንዲሆን ተደርጎ የተሰራው፣ ነጨ ባለ አንድ ፎቅ የአስተዳደር ህንፃ የመዝናኛ
ቦታ ይመስላል፡፡ ቢሮዬ እንደተመለስኩ፣ የቀረኝን እንደምፈልገው አስተካክዬ ጨረስኩ፡፡ የተሰጠኝን ኮምፒውተር ከፍቼ፣ ስለመስሪያ ቤቱ የተሻለ ምስል ይስጡኛል ያልኳቸውን መረጃዎች ለማግኝት ፋይሎች እየከፈትኩ በማንበብ ተጠመድኩ፡፡ ድርጅቱ ትልቅ ራዕይ እንዳለው ተረዳሁ፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተፎካካሪ የመሆንና በሀገራችን ላሉ .
ተመሳሳይ የጨርቃ ጨርቅ ድርጅቶችም የልህቀት ማዕከል መሆን ራዕዩ አድርጎ አስቀምጧል፡፡ ለዚህ ደግሞ ታታሪና ውጤታማ የሆኑ ሰራተኞችን ዋንኛ ግብአት ብቻ ሳይሆኑ፣ ምሰሶና ማገር ናቸው ብሎ ይተነትናል። ሰራተኞቹ ለምን እንደዛ ደስተኛ እንደሆኑ አሁን
ተገለፀልኝ፡፡ አስር ሰዓት ተኩል ሲሆን፣ እንደ አዲስ ጎጆ ወጪ፣ ሳይመሽ
አንድ አንድ ያልገዛኋቸውን የቤት እቃዎች ለመግዛት ቀድሜ ወጣሁ፡፡እቃዎቹን ገዛዝቼ፣ እራት በልቼ ወደ ቤት ገባሁ፡፡ ደስ ሚል ቀን ነበር፡፡ደክሞኝ ስለነበር እንቅልፍ ቶሎ ወሰደኝ፡፡
።።።።።
ስራ ከጀመርኩ ልክ አንድ ወር ሞላኝ፡፡ ስራውና የስራ ከባቢዬ ተስማምቶኛል፡፡ የስራ ፍላጎቴና ተነሳሽነቴ ተመልሶ ከፍ ብሏል፡፡ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ስራዬን በፍጥነት ለማወቅና ለመረዳት
ችያለሁ፡፡ የተለያዩ ፋይሎችን፣ ደብዳቤዎችን አገላብጬ አነበብኩ።
ከሰዎችና ከሰራተኞች ጋር የመተዋወቅና የመቀራረብ ፍላጎቴም ከፍ ብሎ፣ ሰራተኞችን በየክፍሉ እየዞርኩ እየተዋወኩ አናገርኩ፡፡ የስራ ቅልጥፍናዬ ከሰራተኛው ጋር ያለኝ መግባባትና የስራ ተነሳሽነቴ
በአለቃዬም ሆነ በሰራተኛው ከጠበኩት ፍጥነት በላይ ታማኝነትና ከበሬታን አስገኘልኝ፡፡ በየቀኑ ከማከናውናቸው የዕለት ተዕለት ስራዎች በተጨማሪ፣ ድርጅቱ ያስቀመጠውን ራዕይ ለማሳካት፣ ይጠቅማል ያልኳቸውን ለመስራት እሞክራለሁ፡፡
ሰራተኛውንም የድርጅቱን ራዕይ ተገንዝቦ፣ በዛው መጠን እንዲተጋ አነቃቃለሁ፤ እመክራለሁ፡፡ከስኞ እስከ ቅዳሜ እንሰራለን፡፡ ቅዳሜ ግማሽ ቀን ስለሆነ፣
ከነሳሚ ጋር ተያይዘን እንወጣለን፤ ምሳ በልተን እየጠጣን መጫወት ልምድ ሆኗል፡፡ አለቃዬ አንዳንዴ አብረውን ወጥተው ይጋብዙናል፡፡ከቆነጃጅቶች አንዷን ለማጥመድ፣ በደፈናው ሁሉም ላይ መረቤን ዘርግቻለሁ፡፡ ወጣትነቴንና ወንደላጤነቴን እንደ የመጫወቻ ካርድ
አድርጌ እየተጠቀምኩበት ነው፡፡ አሁን በስራዬም በህይወቴም ደስተኛ
ሆኛለሁ፡፡ ዛሬ ሰኞ ነው፡፡ ሁሌ ሰኞ እንደምለብሰው፣ ሙሉ ሱፍ በከረባት
ለብሻለሁ፡፡ የመጀመሪያ ወርሃዊ የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ከእቅድ ጋር
እያነፃፀርኩ እየሰራሁ ነው፡፡
“መግባት ይቻላል...?” ማሂ ቆንጆ ነች፡፡
ሎርድ...!” ሳላስበው ከአፌ አመለጠኝ፡፡ ዛሬ ደግሞ ብሶባታል፡፡ጥቁር ቀሚስ፣ በጥቁር ሂል ጫማ አድርጋለች፡፡ ፀጉሯን ሂውማን ሄር በደንብ ተሰርታለች፡፡ ያልተሸፈኑት ታፋዎቿ ቀይ ፍም መስለው
ተቃቅፈዋል፡፡ እመሃል ግባ ግባ የሚል ስሜት ድንገት ነዘረኝ፡፡
“ምን አልከኝ ያቡ?" አለችኝ፣ ፈገግ ብላ፡፡
“መጠየቁስ ነው ያልኩሽ...”
“ሳይጠየቅማ አይገባም! ሌላ ሰው ቢኖርስ?” ፈገግ አለች፡፡
“ውይ ለካ እንደዛም አለ፡፡ ያለቃ ፀሃፊ መሆንኮ።”ሰምታኝ ይሆን? ተንተባተብኩ፡፡
“ይሄን ደግሞ ማን ነው የሰጠህ?”
“የቱን?” እንዳልገባኝ አብሪያት ዞሬ እያየሁ፡፡
“አበባውን ነዋ፡፡ በናትህ ማናት ያመጣችልህ? ኪ.ኪ.ኪ.”
“እንዴ...! ለምን ማናት አልሽኝ? ምን ማለት ፈልገሽ ነው?”
“ያው ሰሞኑን፣ የግቢውን ሴቶች አየር ስለተቆጣጠርከው፣ አንዷ
አምጥታልህ ይሆናል ብዬ ነዋ! ኪ.ኪ.ኪ...”
“አንቺ ደግሞ ትቀልጂያለሽ፡፡ እራሴ ነኝ ያመጣሁት፡፡ እንዳንቺ ያለች አበባ ምትመስል ፀሀፊ ባይመድቡልኝም፣ ቢሮዬን በአበባ ላሳምር ብዬ ነው፡፡”
“እረ ባክህ..! ኪ.ኪ.ኪ... እኔ ምልህ ያቡ፣ በናትህ ዛሬም ላስቸግርህ?”
“ምን ልታዘዝ? ደግሞ ላንቺ...”
“ማታ ስንወጣ ምሄድበት ነበረኝ፤ ታደርሰኛለህ? እንዲህ ለብሼ በታክሲ መሄድ...” ብላ ዝቅ ብላ ዳሌዋንና ጫማዋን በዐይኗ ጋበዘችኝ፡፡ዕይኖቿን ተከትዬ ቀያይ ታፋዎቿ መሃል ገባሁ፡፡
ድንገት የታፋዎቼ መሃል ሙቀት ሲጨምር፣ እመሃሉ እሳተ ሲለኮስ ተሰማኝ፡፡ ሳላስበው፣
“ግን ዛሬ ትንሽ አመሻለሁ፤” አልኩኝ፡፡
“እስከ ስንት ሰዐት?”
“እስከ አስራ ሁለት፣” ካፈርኩ አይመልሰኝ፡፡
“ችግር የለም እጠብቅሃለው።”
ካላስመሸሁሽ፣ እሺ እሽኝሻለሁ።”
ከማሂላ ጋር ተቀራርበናል፡፡ በፍጥነት ቤተሰብ አድርጋኛለች፡፡በተደጋጋሚ እንድሸኛት ጠይቃኝ፣ አድርሻታለሁ፡፡ ሻይ ቡናም፣ እራትም ጋብዤያታለሁ፡፡ እንድገባ በሯን እንደከፈተችልኝ ገብቶኛል፡፡ እንዳልገባኝ አልፈዋለሁ፡፡ ማታ ሸኝቼያት ስትወርድ በከፊል ከንፈሬን ስማኝ
ትወርዳለች፡፡ ምንም እንዳልተፈጠረ ደና እደሪ ብያት እሄዳለሁ።መጀመሪያ ቀን የደነገጠላት ልቤ ስትቀርበኝ ቀዝቀዝ አለ፡፡ ከእርሷ ይልቅ ወደ ሜሪ እንዳደላ ይሰማኛል፡፡ ከሜሪ ጋር ብዙ የመገናኘት እድል የለኝም፡፡ በአካል አንዴ ብቻ ነው አግኝቼ ሻይ ቡና ያልኳት፡፡ በስልክ
ግን ብዙ እናወራለን፡፡ ፍላጎት እንዳላት፣ ቢጫ መብራት አሳይታኛለች፡፡ ውስጤ ለሜሪ ስላደላ
እርሷን ለመጠበቅ፣ የማሂን የተከፈተ በር እንዳላየ፣ እንዳልገባው፣ አልፈዋለሁ፡፡ ዛሬ ግን በጣም ልዩ ሆናለች፡፡ ስሜቴን አላወሰችው። እንኳን ተከፍቶ፣ አንኳኩቶም መግባትን
ያስመኛል፡፡ ቀኑ አልመሽ አለኝ፡፡ ተሰምቶኝ የማያውቅ የቅንዝረኝነት ስሜት ቀኑን
ሙሉ ሲላወስብኝ ዋለ፡፡ ሊበርድልኝ ልቀዘቅዝ አልቻልኩም፡፡
እንደምንም ከስሜቴ ጋር ታግዬ ሃሳቤን አሰባሰብኩና መስራት ጀመርኩ፣ ኮሪደሩ ላይ ጫጫታ ተሰማኝ፡፡ ጆሮዬን ጣል አድርጌ አዳመጥኩ፡፡ የኤፍሬም ድምፅ ነው፡፡ ጫጫታው ሲበዛ ተነስቼ ወጣሁ፡፡
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ያስመኛል፡፡ ቀኑ አልመሽ አለኝ፡፡ ተሰምቶኝ የማያውቅ የቅንዝረኝነት ስሜት ቀኑን
ሙሉ ሲላወስብኝ ዋለ፡፡ ሊበርድልኝ ልቀዘቅዝ አልቻልኩም፡፡
እንደምንም ከስሜቴ ጋር ታግዬ ሃሳቤን አሰባሰብኩና መስራት ጀመርኩ፣ ኮሪደሩ ላይ ጫጫታ ተሰማኝ፡፡ ጆሮዬን ጣል አድርጌ አዳመጥኩ፡፡ የኤፍሬም ድምፅ ነው፡፡ ጫጫታው ሲበዛ ተነስቼ ወጣሁ፡፡
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👏1
Forwarded from 📱SAMSUNG Mobile Store (SMS) (DERAMING)
የእርዳታ ጥሪ
በእግዚአብሄር በአላህ ሼር አድርጉት ‼️😭
• እናቷ እያለቀሰችየነገረችን 😭
• በጎላ ሠፈር ዮሴፍ ሞተር ቤት ፊትለፊት መንደር የምትኖር እፁብ አየለ ትባላለች የ15 ዓመት ወጣት የ8ኛ ክፍል ተማሪ ነች በጭንቅላት ቲቢ እና በጭንቅላት እጢ መሠቃየት ከጀመረች 6 ወሯ ነው ቅ/ጳውሎስ ሆስፒታል ከተኛች 3 ወሯ አትሰማም አትናገርም ! የእናትን ነገር ታቁታላቹ ቀን ሌሊት እያለቀሰች ነው !
ወላጅ እናቷ እዛው እየዋለች እያደረች የምታስታምም ስትሆን አሁን ግን መድሀኒት መግዣ መንቀሳቀሻ ቀለብ ቀሪ ቤተሠብ ማስተዳደር አልቻልኩም ልጄን የተሻለ ሕክምና የተሻለ መድሀኒት እንድታገኝ በሀሳብም በገንዘብም እርዳታችሁ በፈጣሪ ስም አይለየኝ ትላለች ወላጅ እናቷ እያለቀሠች
094 021 5213 ንብረት በሬቻ / እናቷ
1000030804398 ንብረት በሬቻ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
በእግዚአብሄር በአላህ ሼር አድርጉት ‼️😭
• እናቷ እያለቀሰችየነገረችን 😭
• በጎላ ሠፈር ዮሴፍ ሞተር ቤት ፊትለፊት መንደር የምትኖር እፁብ አየለ ትባላለች የ15 ዓመት ወጣት የ8ኛ ክፍል ተማሪ ነች በጭንቅላት ቲቢ እና በጭንቅላት እጢ መሠቃየት ከጀመረች 6 ወሯ ነው ቅ/ጳውሎስ ሆስፒታል ከተኛች 3 ወሯ አትሰማም አትናገርም ! የእናትን ነገር ታቁታላቹ ቀን ሌሊት እያለቀሰች ነው !
ወላጅ እናቷ እዛው እየዋለች እያደረች የምታስታምም ስትሆን አሁን ግን መድሀኒት መግዣ መንቀሳቀሻ ቀለብ ቀሪ ቤተሠብ ማስተዳደር አልቻልኩም ልጄን የተሻለ ሕክምና የተሻለ መድሀኒት እንድታገኝ በሀሳብም በገንዘብም እርዳታችሁ በፈጣሪ ስም አይለየኝ ትላለች ወላጅ እናቷ እያለቀሠች
094 021 5213 ንብረት በሬቻ / እናቷ
1000030804398 ንብረት በሬቻ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
👍1
#ቁጭት
መውደድን አርሰን ቆፍረን.. ፍቅርን ነበር የዘራነው
ትውውቅን ተክለን ኮትኩተን..ደስታን ነበር ያሳደግነው
የጥርጣሬ ነቀዝ በልቶት...ገና ሳይበስል ቆረጥነው::
ለካ መለየት እንዲህ...ሰውን በቁሙ ይበላል?
ለካ 'ሚወዱት ሲርቅ...ዓለም በሙሉ ያስጠላል?
ለካንስ ትርፉ ፀፀት ነው...ብቼኝነትም ያደክማል!?
አጥንቴ ቀረልሽ ፍቅሬ..ወጣሁልሽ ከሰው ተራ
ብቻየን ማውራት ጀመርኩኝ..አበደ ተብሎ ተወራ፡፡
ግዴለም ስጋ ቢስ ልሁን...እብደቴን ሰው ይወቅብኝ
አንቺ ካለሽ ነው ምኖረው -
ብቻ አንቺን ክፉ አይይብኝ
ብቻ አንቺን ክፉ አይንካብኝ፡፡
አንቺ ካለሽ ነው ምኖረው...እላለሁኝ ደሞ አላፍርም
በቁሙ ከሚነገላጀጅ
ሐዘን ደስታውን ከረሳ...የተቀበረ አይሻልም!?
ቢሆንም ሞት አልፈልግም...መንቀዋለሉ ይሻለኛል
ሰማይ ቤት እንዳንቺ ያለ.ፍጥረትስ እንዴት ይገኛል!?
ፍቅራችን ማበብ ሲጀምር....እንዳይከስም ያልደከመ
የፈስስን ውሐ ላያፍስ...የሰማይ ላሙን እያለመ
አለ ስላሙ ሲናጋ..ልቤ ትዝታን እያከመ::
ትዝ ይልሻል መቼም ፍቅሬ.. ፍቅራችን ምን እንደነበር?
ተዝቆ ማያልቅ የሚመስል
ዕልፍ አዕላፍ ደስታ..ከፊታችን ሲደረደር
ተስገብግበን ስንቋደስ
አንቺ በስሜ ትምይ ነበር
እኔ በስምሽ እምል ነበር፡፡
የፍቅር መልአክ ኮርኩሮሽ..ሰማይ እያየሽ ስትስቂ
የመውደድ ብርሐን ተገልጦ.. አይኔን እያየሽ ስትቦርቂ፣
ይመስለኝ ነበር ፅድቅነት
የገባሁ ከምድር ገነት፡፡
ታዲያ አሁን ያ ህልም መሳይ..የህይወት ብርሐን ደብዝዞ
ያልበሰለው የፍቅር እሸት...እንዳይበላ ጎምዝዞ
ብቻየን አስቀረኝ እኔን.. ትዝታሽን ብቻ አስይዞ፡፡
እኔ ምለው የኔ ስስት፣
የኔ ፅልመት፣
የኔ ብርሐን፤
እንዲያ በደስታ እንዳልፈካን
በሳቅ እንዳላውካካን፣
ካንቺ ጋር አብሮ የራቀኝ.. አለኝ የምለው ዘመዴ
ከንፈሬ የማይገለጥ...ሳቅ እምቢ ያለኝ ከሆዴ
የሳቅም ጡር አለው እንዴ!?
ግዴለም ሳቅ ይቅርብኝ...ሳቄ በለቅሶ ይተካ
መኖርሽን በማሰብ ብቻ...ልቤ እያነባ ይፍካ፡፡
በእጅ የያዙት ወርቅ እንዲሉ...ችላ ያልነው እንደዋዛ
ጠብታዋ ባህር ሆና
ያማረን ጎጆ ስታፈርስ...የሞቀውን አቀዝቅዛ፣
የአብሮነት ኑሮ ምቾቱ...የትካዜ ጎርበጥባጣው
የብቼኝነት ህመሙ ሲለያዩ ነው የሚሰማው፡፡
ስጋና አጥንቴ ተጣብቀው...ደስታ ርቆብኝ ቢያዩኝ
ህመምህን ንገረን' ብለው...ጓደኞቼ እንኳን ጠየቁኝ፡፡
ራሴን
ሆዴን
እግሬን
ልቤን.......
አልልም ጉዳታቸው አይሰማኝም
ምንድን ነው ሚያምህ?” አትበሉኝ... እኔኮ ስሜት የለኝም
የሆድ ቁርጠት...ራስ ምታት...ብሎ ነገር አይገባኝም፡፡
አንድ በሽታ ብቻ ያለኝ
አንድ ሐኪም ብቻ የሚያድነኝ
እኔ የሷ በሽተኛ...እኔ የሷ ታካሚ ነኝ፡፡
እናማ የኔ ሐኪም...የኔ ህመም የኔ ፈዋሽ
በእንባየ የታጠበውን...ነጭ ጋዎንሽን ለብሰሽ
እንደ ድሮው ተፍለቅላቂ..ይመርብሽ ልይሽ ደምቀሽ፡፡
እኔ ግን የኔ ሩቅ
ካንቺ ከተለየሁ...ከተራራቅሁ ወዲህ
ሆኛለሁ ቀልበ ቢስ...ሆኛለሁ ልብ ውልቅ
ሲያጫውቱኝ የማለቅስ...ሲሰድቡኝ የምስቅ፡፡
ሆኛለሁ ብቸኛ... ሆኛለሁ ልብ አድርቅ
ሲርቁኝ የማልቀርብ...ሲጠጉኝ የምርቅ፡፡
🔘በሙሉቀን🔘
መውደድን አርሰን ቆፍረን.. ፍቅርን ነበር የዘራነው
ትውውቅን ተክለን ኮትኩተን..ደስታን ነበር ያሳደግነው
የጥርጣሬ ነቀዝ በልቶት...ገና ሳይበስል ቆረጥነው::
ለካ መለየት እንዲህ...ሰውን በቁሙ ይበላል?
ለካ 'ሚወዱት ሲርቅ...ዓለም በሙሉ ያስጠላል?
ለካንስ ትርፉ ፀፀት ነው...ብቼኝነትም ያደክማል!?
አጥንቴ ቀረልሽ ፍቅሬ..ወጣሁልሽ ከሰው ተራ
ብቻየን ማውራት ጀመርኩኝ..አበደ ተብሎ ተወራ፡፡
ግዴለም ስጋ ቢስ ልሁን...እብደቴን ሰው ይወቅብኝ
አንቺ ካለሽ ነው ምኖረው -
ብቻ አንቺን ክፉ አይይብኝ
ብቻ አንቺን ክፉ አይንካብኝ፡፡
አንቺ ካለሽ ነው ምኖረው...እላለሁኝ ደሞ አላፍርም
በቁሙ ከሚነገላጀጅ
ሐዘን ደስታውን ከረሳ...የተቀበረ አይሻልም!?
ቢሆንም ሞት አልፈልግም...መንቀዋለሉ ይሻለኛል
ሰማይ ቤት እንዳንቺ ያለ.ፍጥረትስ እንዴት ይገኛል!?
ፍቅራችን ማበብ ሲጀምር....እንዳይከስም ያልደከመ
የፈስስን ውሐ ላያፍስ...የሰማይ ላሙን እያለመ
አለ ስላሙ ሲናጋ..ልቤ ትዝታን እያከመ::
ትዝ ይልሻል መቼም ፍቅሬ.. ፍቅራችን ምን እንደነበር?
ተዝቆ ማያልቅ የሚመስል
ዕልፍ አዕላፍ ደስታ..ከፊታችን ሲደረደር
ተስገብግበን ስንቋደስ
አንቺ በስሜ ትምይ ነበር
እኔ በስምሽ እምል ነበር፡፡
የፍቅር መልአክ ኮርኩሮሽ..ሰማይ እያየሽ ስትስቂ
የመውደድ ብርሐን ተገልጦ.. አይኔን እያየሽ ስትቦርቂ፣
ይመስለኝ ነበር ፅድቅነት
የገባሁ ከምድር ገነት፡፡
ታዲያ አሁን ያ ህልም መሳይ..የህይወት ብርሐን ደብዝዞ
ያልበሰለው የፍቅር እሸት...እንዳይበላ ጎምዝዞ
ብቻየን አስቀረኝ እኔን.. ትዝታሽን ብቻ አስይዞ፡፡
እኔ ምለው የኔ ስስት፣
የኔ ፅልመት፣
የኔ ብርሐን፤
እንዲያ በደስታ እንዳልፈካን
በሳቅ እንዳላውካካን፣
ካንቺ ጋር አብሮ የራቀኝ.. አለኝ የምለው ዘመዴ
ከንፈሬ የማይገለጥ...ሳቅ እምቢ ያለኝ ከሆዴ
የሳቅም ጡር አለው እንዴ!?
ግዴለም ሳቅ ይቅርብኝ...ሳቄ በለቅሶ ይተካ
መኖርሽን በማሰብ ብቻ...ልቤ እያነባ ይፍካ፡፡
በእጅ የያዙት ወርቅ እንዲሉ...ችላ ያልነው እንደዋዛ
ጠብታዋ ባህር ሆና
ያማረን ጎጆ ስታፈርስ...የሞቀውን አቀዝቅዛ፣
የአብሮነት ኑሮ ምቾቱ...የትካዜ ጎርበጥባጣው
የብቼኝነት ህመሙ ሲለያዩ ነው የሚሰማው፡፡
ስጋና አጥንቴ ተጣብቀው...ደስታ ርቆብኝ ቢያዩኝ
ህመምህን ንገረን' ብለው...ጓደኞቼ እንኳን ጠየቁኝ፡፡
ራሴን
ሆዴን
እግሬን
ልቤን.......
አልልም ጉዳታቸው አይሰማኝም
ምንድን ነው ሚያምህ?” አትበሉኝ... እኔኮ ስሜት የለኝም
የሆድ ቁርጠት...ራስ ምታት...ብሎ ነገር አይገባኝም፡፡
አንድ በሽታ ብቻ ያለኝ
አንድ ሐኪም ብቻ የሚያድነኝ
እኔ የሷ በሽተኛ...እኔ የሷ ታካሚ ነኝ፡፡
እናማ የኔ ሐኪም...የኔ ህመም የኔ ፈዋሽ
በእንባየ የታጠበውን...ነጭ ጋዎንሽን ለብሰሽ
እንደ ድሮው ተፍለቅላቂ..ይመርብሽ ልይሽ ደምቀሽ፡፡
እኔ ግን የኔ ሩቅ
ካንቺ ከተለየሁ...ከተራራቅሁ ወዲህ
ሆኛለሁ ቀልበ ቢስ...ሆኛለሁ ልብ ውልቅ
ሲያጫውቱኝ የማለቅስ...ሲሰድቡኝ የምስቅ፡፡
ሆኛለሁ ብቸኛ... ሆኛለሁ ልብ አድርቅ
ሲርቁኝ የማልቀርብ...ሲጠጉኝ የምርቅ፡፡
🔘በሙሉቀን🔘
#የታካሚው_ማስታወሻ
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
እንደምንም ከስሜቴ ጋር ታግዬ ሃሳቤን አሰባሰብኩና መስራት ጀመርኩ፣ ኮሪደሩ ላይ ጫጫታ ተሰማኝ፡፡ ጆሮዬን ጣል አድርጌ አዳመጥኩ፡፡ የኤፍሬም ድምፅ ነው፡፡ ጫጫታው ሲበዛ ተነስቼ ወጣሁ፡፡
“አንቺ እኔን ሌባ እያልሽኝ ነው? የእንትን ልጅ! እገልሻለሁ እገልሻለሁ! እኔ ወንድ አይደለሁም!”
“ልቀቀኝ! ልቀቀኝ! እደፋታሁ! ልታሰራ! ልታሰር...! ልቀቀኝ ባክህ!” ሳሚ ኤፍሬምን ከእነርሱ ቢሮ እጆቹና ወገቡን እንደማቀፍ ይዞ እየገፋ ያስወጣዋል። ሁሉም በቢሮው በር ብቅ ብቅ ብሎ ይመለከታል።ሳሚ ኤፍሬምን ከህንፃው አረጋግቶት፣ አስወጥቶ፣ እየሳቀ ተመለሰ፡፡
“ምንድ ነው? ከማን ጋር ነው?”
“ሆ ...! ከቤቲ ጋር ነዋ፡፡ ባልተባለው ነገር እኮ ነው ሚጮኸው።ሰሞኑን ደግሞ ወፈፌነቱ ተነስቶበታል፡፡” አለኝ ወደ ቢሮው እየተመለሰ፡፡ቢሮዬ ገባሁ፡፡ ሳሚ ከተናገረው “ወፈፌነቱ ተነስቶበታል፤” ያለው አረፍተ ነገር ውስጤ ቀረ፡፡ ኤፍሬም ከእሩቅ ሲያዩት የተረጋጋ ሰው ይመስላል፡፡
ቀረብ ሲሉት ግን በጣም ብስጩና በቀላሉ ወደ ፀብ ሚገባ ባህሪ አለው።
ይህን እንደኔ ሌላም ሰው ተገንዝቦታል ማለት ነው? ለኔ ግን ጭንቅላቱ
ከባህሪው ይበልጥብኛል፡፡ እንደባህሪው ተለማምጬ አሰራዋለሁ፡፡ ይህን
ፀባዩን ማረቅ ቢቻል ጥሩ ደረጃ ሚደርስ ልጅ ነው፡፡ እስከ አስራ አንድ ሰአት እንደነገሩ እየሰራሁ ቆየሁና ለማሂ ደወልኩላት፡፡
“ማሂላ አንወጣም?”
“እንዴ! አስራ ሁለት ሰዓት አላልክም ነበር?”
“ጨረስኩኛ፡፡ በዛ ላይ ደግሞ ናፈቅሺኝ...”
“እሺ መጣሁ፤ ጠብቀኝ! አስር ደቂቃ ብቻ!” ቢሮዬን ዘግቼ እርሷን መጠበቅ ጀመርኩ፡፡ አልቆየችም፡፡ ከቢሮ እየወጣን፣
“የት ነው ግን ወይን ምጋብዝሽ?”
“እንዴ... እምሄድበት አለኝ ብዬሃለው እኮ!”
“እሱማ ብለሺኛል፡፡ እኔ ግን እንዲህ አምሮብሽ ሳልጋብዝሽ ዝም ብዬ አልሸኝሽም፡፡”
“እንዴ... ማልቀርበት ቀጠሮኮ አለኝ፡፡”
“ማን ቅሪ አለሽ? ትንሽ ቆይተሽ ትሄጂያለሽ፡፡ የት ልጋብዝሽ?
ኤግልስ?”
“ደረቅ ነህ እሺ፡፡ ግን ትንሽ ነው ምንቆየው።”
“ችግር የለውም፡፡”
ዛሬ ግን ምን ሆነህ ነው እንዲህ በጣም የተሟዘዝከው?”
ፍቅር ይዞኝ!”
“ምን...? አንተን...? ኪ.ኪ.ኪ...” ቆማ ሳቋን ለቀቀችው:: .
“ምነው? እሺ መኪና ውስጥ ግቢና ትስቂያለሽ፡፡ ከዚ ግቢ ቶሉ እንውጣ፡፡” ገብታ እንደተቀመጠች፣
የመኪናህ ሽታ ደስ ሲል! ደግሞ ሁሌም ንፁህ ነች፡፡ ጎበዝ ነህ ቢሮ አያያዝህም፣ እንደ ወንዶች አይደለህም፡፡” መኪናዋን እንደሚገዝ ሰው ዞራ እያየች፡፡
“ቆይ ግን ምን ለማለት ነው? ወንድ ልጅ ንፁህ ነገር አይወድለትም?”
“አልወጣኝም! ግን የሳሚን መኪና አታያትም? የቆሻሻ ቅርጫት አስመስሏት... ኪ.ኪ...ኪ...”
“እሺ ቆይ፣ እኔ አላምርም እንዴ? ሁሌም ቢሮህ፣ መኪና ምናምን ምትዪኝ፡፡ ለነገሩ አንችን የመሰለች፣ ግማሽ መላዕክ፣ ግማሽ ሰው፣ የሆነች ቆንጅዬ ጭኜ ከሄድኩኝ፣ ባላምርም አምራለሁ።”
ኪ.ኪ.ኪ... ኧረ መሞጣሞጥ...፣ ዝምተኛ አልነበርክ እንዴ...? ሳሚ አጋባብህ ማለት ነው...?”
“ምን ያጋባብኛል.…? ስራ ቦታ ነው ብዬ ዝም አልኩ እነጂ፣ በውስጤ ከገባሽ ቆየሽ፡፡”
“ምን ማለት ነው?”
“እንግዲ ዛሬ አፈነዳዋለሁ፡፡ ካለመናገር ደጅ አዝማችነት ይቀራል፡፡ በደንብ ተመችተሽኛል፤ ወድጄሻለሁ...”
“ምን...?!”
“አዎ! እስካሁንም ፈርቼሽ ነው!”
“እንዴ አንተ ግን የ'ውነት ሳትዋሽ ሚስት ወይም ፍቅረኛ የለችህም?”
“አዎ! እግዚአብሄር ይመስገን የለኝም።”
“ኪ.ኪ.ኪ... አንተ..? ጭራሽ “እግዚአብሄር ይመስገን የለኝም፡፡'?››
“እውነቴን ነዋ...!፡፡ ቆይ ኖሮኝ ቢሆን፣ አሁን አንቺን የመሰለች ልዕልት ምን አደርግ ነበር? እንኳን አልኖረኝ! አዎ እግዚአብሄር ይመስገን!”
“...ኪ...ኪ...፣ኧረ የዛሬ ምላስ...?”
“ምነው? ባለፈው በጌታ ምን ሆነህ ነው እንዲህ ዝም ምትለው እንዳላልሽኝ፣ ዛሬ ደግሞ፣ በጌታ ስም ይዤሃለው ዝም በልልኝ ልትዪኝ ነው እንዴ?”
| “..ኪ..ኪ...ኪ ኧረ አልልህም! እዚህ ግቢ እንኳን ዝም ተብሎ፣ ተቃጥለንም አልቻልንም፡፡ ግን እንዴት አንተን የመሰለ ልጅ እስካሁን ቢያንስ ፍቅረኛ የለውም?”
“ውይ እንደዛ ከሆነማ፣ እንቺን የመሰለች ልዕልት አግብተሻል ማለት ነው፡፡”
ኪ.ኪ.ኪ...፣ ፍሬቻ አብራ እንጂ፣ በዚህ ጋር ወደ ቀኝ ነንኮ ጠፋብህ እንዴ?”
መኪና አቁመን፣ አንደኛ ፎቅ ላይ ሸሸግ ያለቦታ መርጠን ተቀመጥን፡፡ እራት በልተን ወይን እየጠጣን የሞቀ ጨዋታ ያዝን። ምትሄድበት አልነበረም ወይም እረስታዋለች፡፡ እኔም እንዳላስታወስ ሰው
በጨዋታ ላይ ጨዋታ እያመጣሁባት ዝም አልኳት። ዛሬ እንድትሄድብኝ አልፈለኩም፡፡ እየመሸ ሲመጣ የቤቱ ብርሃን መደብዘዝ ጀመረ። ቀን
እንደዛ ምራቄን ስውጥ የዋልኩበት ታፋዎቿን በሳቆቼ እያሳበብኩ
እዳብሳቸው ጀመር፡፡ መጠጡ ሞቅ እያለኝ ሲመጣ፣ ከመዳበስ አልፌ
እጄን መሃል ለመሃል ወሸኩት፡፡ ምንም እንዳልተፈጠረ ትጫወታለች፣ትስቃለች፡፡ ታፋዎቿ ያቃጥላሉ፡፡ ውስጤ በስሜት ነደደ፡፡
ሂሳብ ከፍዬ ወደ ቤት ወጣን፡፡ መኪናዬ ውስጥ እንደገባን፣
“ዛሬ ካንቺ መለየት አልፈልግም!” አልኳት፡፡
“ኪ.ኪ.ኪ...፣ እና ምን ልታደርግ ነው?”
“ወይ እቤትሽ አብሬሽ ሄዳለሁ ወይም አብረሽኝ እቤቴ ትሄጂያለሽ፡፡ ዛሬ ካንቺ ተለይቼ ማደር አልችልም፡፡”
“ኪ.ኪ.ኪ. ቆይ ምንድነው አላማህ? አከራዬ ቤቴ ጎረምሳ አመጣሽብኝ ብለው በጥዋት ከቤት እንዲያባርሩኝ ነው?”
“እኔ ቤት እናድራለታን እንጂ፣ እንድትባረሪብኝማ አልፈልግም፡፡” ወደ እኔ ቤቴ መንዳት ጀመርኩ፣
“አንተ ደግሞ፣ ዝም ተብሎ በድንገት ወጥቶ ማደር አለ እንዴ?” አንገራገረች፡፡ መኪናውን ድንገት መንገድ ዳር አቁሜ፣ ፊቷን ላለማየት መሪው ላይ ተጎንብሼ፣ መለመን ጀመርኩ፤
“ንግስትዬ ፕሊስ፣ እንደዚህ ሆኜ አላውቅም! በጣም ከባድ ስሜት
እየተሰማኝ ነው፡፡ ፕሊስ?!” ብያት ማላውቀውን እያልኩ ለመንኳት፡፡
“እሺ፣ ነገ ስራ ምን ለብሼ ገባለሁ? ይሄን ለብሼ?
ምን ይሉኛል? ውጪ እንዳደርኩ ያስታውቃልኮ፣ አላደርገውም፡፡”
“ንግስትዬ ለሱ ችግር የለውም፤ ከፈለግሽ አሁኑኑ ሌላ ልብስ
ገዝተን እንግባ፡፡”
“ያምሃል እንዴ አንተ? በዚህ ሰዐት የምን ክፍት ሱቅ አለ? ሰዐቱን አይተኸዋል?”
“እሺ በቃ፣ እኔ ጥዋት በፈለግሽው ሰዐት እቤት አደርስሽና ቀይረሽ ስራ እንገባለን፡፡
እስከዛሬ ፈርቼሽ፣ ስሜቴን አፍኜው ስለቆየሁ ነው? ፕሊስ ውቢት ተረጂኝ፡፡” እትት በረደኝ ብዬ ዘፈንኩላት፡፡ ፍቅርሽ
ሆዴ ገብቶ ያንዘፈዝፈኛል አልኳት፡፡ በመጨረሻም ተስማማች፣ እኔ ጋር
አደረች፡፡
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
እንደምንም ከስሜቴ ጋር ታግዬ ሃሳቤን አሰባሰብኩና መስራት ጀመርኩ፣ ኮሪደሩ ላይ ጫጫታ ተሰማኝ፡፡ ጆሮዬን ጣል አድርጌ አዳመጥኩ፡፡ የኤፍሬም ድምፅ ነው፡፡ ጫጫታው ሲበዛ ተነስቼ ወጣሁ፡፡
“አንቺ እኔን ሌባ እያልሽኝ ነው? የእንትን ልጅ! እገልሻለሁ እገልሻለሁ! እኔ ወንድ አይደለሁም!”
“ልቀቀኝ! ልቀቀኝ! እደፋታሁ! ልታሰራ! ልታሰር...! ልቀቀኝ ባክህ!” ሳሚ ኤፍሬምን ከእነርሱ ቢሮ እጆቹና ወገቡን እንደማቀፍ ይዞ እየገፋ ያስወጣዋል። ሁሉም በቢሮው በር ብቅ ብቅ ብሎ ይመለከታል።ሳሚ ኤፍሬምን ከህንፃው አረጋግቶት፣ አስወጥቶ፣ እየሳቀ ተመለሰ፡፡
“ምንድ ነው? ከማን ጋር ነው?”
“ሆ ...! ከቤቲ ጋር ነዋ፡፡ ባልተባለው ነገር እኮ ነው ሚጮኸው።ሰሞኑን ደግሞ ወፈፌነቱ ተነስቶበታል፡፡” አለኝ ወደ ቢሮው እየተመለሰ፡፡ቢሮዬ ገባሁ፡፡ ሳሚ ከተናገረው “ወፈፌነቱ ተነስቶበታል፤” ያለው አረፍተ ነገር ውስጤ ቀረ፡፡ ኤፍሬም ከእሩቅ ሲያዩት የተረጋጋ ሰው ይመስላል፡፡
ቀረብ ሲሉት ግን በጣም ብስጩና በቀላሉ ወደ ፀብ ሚገባ ባህሪ አለው።
ይህን እንደኔ ሌላም ሰው ተገንዝቦታል ማለት ነው? ለኔ ግን ጭንቅላቱ
ከባህሪው ይበልጥብኛል፡፡ እንደባህሪው ተለማምጬ አሰራዋለሁ፡፡ ይህን
ፀባዩን ማረቅ ቢቻል ጥሩ ደረጃ ሚደርስ ልጅ ነው፡፡ እስከ አስራ አንድ ሰአት እንደነገሩ እየሰራሁ ቆየሁና ለማሂ ደወልኩላት፡፡
“ማሂላ አንወጣም?”
“እንዴ! አስራ ሁለት ሰዓት አላልክም ነበር?”
“ጨረስኩኛ፡፡ በዛ ላይ ደግሞ ናፈቅሺኝ...”
“እሺ መጣሁ፤ ጠብቀኝ! አስር ደቂቃ ብቻ!” ቢሮዬን ዘግቼ እርሷን መጠበቅ ጀመርኩ፡፡ አልቆየችም፡፡ ከቢሮ እየወጣን፣
“የት ነው ግን ወይን ምጋብዝሽ?”
“እንዴ... እምሄድበት አለኝ ብዬሃለው እኮ!”
“እሱማ ብለሺኛል፡፡ እኔ ግን እንዲህ አምሮብሽ ሳልጋብዝሽ ዝም ብዬ አልሸኝሽም፡፡”
“እንዴ... ማልቀርበት ቀጠሮኮ አለኝ፡፡”
“ማን ቅሪ አለሽ? ትንሽ ቆይተሽ ትሄጂያለሽ፡፡ የት ልጋብዝሽ?
ኤግልስ?”
“ደረቅ ነህ እሺ፡፡ ግን ትንሽ ነው ምንቆየው።”
“ችግር የለውም፡፡”
ዛሬ ግን ምን ሆነህ ነው እንዲህ በጣም የተሟዘዝከው?”
ፍቅር ይዞኝ!”
“ምን...? አንተን...? ኪ.ኪ.ኪ...” ቆማ ሳቋን ለቀቀችው:: .
“ምነው? እሺ መኪና ውስጥ ግቢና ትስቂያለሽ፡፡ ከዚ ግቢ ቶሉ እንውጣ፡፡” ገብታ እንደተቀመጠች፣
የመኪናህ ሽታ ደስ ሲል! ደግሞ ሁሌም ንፁህ ነች፡፡ ጎበዝ ነህ ቢሮ አያያዝህም፣ እንደ ወንዶች አይደለህም፡፡” መኪናዋን እንደሚገዝ ሰው ዞራ እያየች፡፡
“ቆይ ግን ምን ለማለት ነው? ወንድ ልጅ ንፁህ ነገር አይወድለትም?”
“አልወጣኝም! ግን የሳሚን መኪና አታያትም? የቆሻሻ ቅርጫት አስመስሏት... ኪ.ኪ...ኪ...”
“እሺ ቆይ፣ እኔ አላምርም እንዴ? ሁሌም ቢሮህ፣ መኪና ምናምን ምትዪኝ፡፡ ለነገሩ አንችን የመሰለች፣ ግማሽ መላዕክ፣ ግማሽ ሰው፣ የሆነች ቆንጅዬ ጭኜ ከሄድኩኝ፣ ባላምርም አምራለሁ።”
ኪ.ኪ.ኪ... ኧረ መሞጣሞጥ...፣ ዝምተኛ አልነበርክ እንዴ...? ሳሚ አጋባብህ ማለት ነው...?”
“ምን ያጋባብኛል.…? ስራ ቦታ ነው ብዬ ዝም አልኩ እነጂ፣ በውስጤ ከገባሽ ቆየሽ፡፡”
“ምን ማለት ነው?”
“እንግዲ ዛሬ አፈነዳዋለሁ፡፡ ካለመናገር ደጅ አዝማችነት ይቀራል፡፡ በደንብ ተመችተሽኛል፤ ወድጄሻለሁ...”
“ምን...?!”
“አዎ! እስካሁንም ፈርቼሽ ነው!”
“እንዴ አንተ ግን የ'ውነት ሳትዋሽ ሚስት ወይም ፍቅረኛ የለችህም?”
“አዎ! እግዚአብሄር ይመስገን የለኝም።”
“ኪ.ኪ.ኪ... አንተ..? ጭራሽ “እግዚአብሄር ይመስገን የለኝም፡፡'?››
“እውነቴን ነዋ...!፡፡ ቆይ ኖሮኝ ቢሆን፣ አሁን አንቺን የመሰለች ልዕልት ምን አደርግ ነበር? እንኳን አልኖረኝ! አዎ እግዚአብሄር ይመስገን!”
“...ኪ...ኪ...፣ኧረ የዛሬ ምላስ...?”
“ምነው? ባለፈው በጌታ ምን ሆነህ ነው እንዲህ ዝም ምትለው እንዳላልሽኝ፣ ዛሬ ደግሞ፣ በጌታ ስም ይዤሃለው ዝም በልልኝ ልትዪኝ ነው እንዴ?”
| “..ኪ..ኪ...ኪ ኧረ አልልህም! እዚህ ግቢ እንኳን ዝም ተብሎ፣ ተቃጥለንም አልቻልንም፡፡ ግን እንዴት አንተን የመሰለ ልጅ እስካሁን ቢያንስ ፍቅረኛ የለውም?”
“ውይ እንደዛ ከሆነማ፣ እንቺን የመሰለች ልዕልት አግብተሻል ማለት ነው፡፡”
ኪ.ኪ.ኪ...፣ ፍሬቻ አብራ እንጂ፣ በዚህ ጋር ወደ ቀኝ ነንኮ ጠፋብህ እንዴ?”
መኪና አቁመን፣ አንደኛ ፎቅ ላይ ሸሸግ ያለቦታ መርጠን ተቀመጥን፡፡ እራት በልተን ወይን እየጠጣን የሞቀ ጨዋታ ያዝን። ምትሄድበት አልነበረም ወይም እረስታዋለች፡፡ እኔም እንዳላስታወስ ሰው
በጨዋታ ላይ ጨዋታ እያመጣሁባት ዝም አልኳት። ዛሬ እንድትሄድብኝ አልፈለኩም፡፡ እየመሸ ሲመጣ የቤቱ ብርሃን መደብዘዝ ጀመረ። ቀን
እንደዛ ምራቄን ስውጥ የዋልኩበት ታፋዎቿን በሳቆቼ እያሳበብኩ
እዳብሳቸው ጀመር፡፡ መጠጡ ሞቅ እያለኝ ሲመጣ፣ ከመዳበስ አልፌ
እጄን መሃል ለመሃል ወሸኩት፡፡ ምንም እንዳልተፈጠረ ትጫወታለች፣ትስቃለች፡፡ ታፋዎቿ ያቃጥላሉ፡፡ ውስጤ በስሜት ነደደ፡፡
ሂሳብ ከፍዬ ወደ ቤት ወጣን፡፡ መኪናዬ ውስጥ እንደገባን፣
“ዛሬ ካንቺ መለየት አልፈልግም!” አልኳት፡፡
“ኪ.ኪ.ኪ...፣ እና ምን ልታደርግ ነው?”
“ወይ እቤትሽ አብሬሽ ሄዳለሁ ወይም አብረሽኝ እቤቴ ትሄጂያለሽ፡፡ ዛሬ ካንቺ ተለይቼ ማደር አልችልም፡፡”
“ኪ.ኪ.ኪ. ቆይ ምንድነው አላማህ? አከራዬ ቤቴ ጎረምሳ አመጣሽብኝ ብለው በጥዋት ከቤት እንዲያባርሩኝ ነው?”
“እኔ ቤት እናድራለታን እንጂ፣ እንድትባረሪብኝማ አልፈልግም፡፡” ወደ እኔ ቤቴ መንዳት ጀመርኩ፣
“አንተ ደግሞ፣ ዝም ተብሎ በድንገት ወጥቶ ማደር አለ እንዴ?” አንገራገረች፡፡ መኪናውን ድንገት መንገድ ዳር አቁሜ፣ ፊቷን ላለማየት መሪው ላይ ተጎንብሼ፣ መለመን ጀመርኩ፤
“ንግስትዬ ፕሊስ፣ እንደዚህ ሆኜ አላውቅም! በጣም ከባድ ስሜት
እየተሰማኝ ነው፡፡ ፕሊስ?!” ብያት ማላውቀውን እያልኩ ለመንኳት፡፡
“እሺ፣ ነገ ስራ ምን ለብሼ ገባለሁ? ይሄን ለብሼ?
ምን ይሉኛል? ውጪ እንዳደርኩ ያስታውቃልኮ፣ አላደርገውም፡፡”
“ንግስትዬ ለሱ ችግር የለውም፤ ከፈለግሽ አሁኑኑ ሌላ ልብስ
ገዝተን እንግባ፡፡”
“ያምሃል እንዴ አንተ? በዚህ ሰዐት የምን ክፍት ሱቅ አለ? ሰዐቱን አይተኸዋል?”
“እሺ በቃ፣ እኔ ጥዋት በፈለግሽው ሰዐት እቤት አደርስሽና ቀይረሽ ስራ እንገባለን፡፡
እስከዛሬ ፈርቼሽ፣ ስሜቴን አፍኜው ስለቆየሁ ነው? ፕሊስ ውቢት ተረጂኝ፡፡” እትት በረደኝ ብዬ ዘፈንኩላት፡፡ ፍቅርሽ
ሆዴ ገብቶ ያንዘፈዝፈኛል አልኳት፡፡ በመጨረሻም ተስማማች፣ እኔ ጋር
አደረች፡፡
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍4❤1🤔1
#የታካሚው_ማስታወሻ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ(MD)
በመጨረሻም ተስማማች፣ እኔ ጋር
አደረች፡፡ በተከፈተልኝ በር ወስኜ መግባት እንዳልከበደኝ፣ አለባበሷና የወይኑ ስሜት ተደማምሮ፣ በድንገት ሰተት ብዬ ገባሁ፡፡ የመጀመሪያ ቀን አይቻት ስደነግጥ እንዲህ በቀላሉ ማገኛት፣ እኔ ላይ እንዲህ ፍላጎት አሳይታ እሺ ምትላኝ አልመሰለኝም ነበር፡፡ በጥዋት ወደ ቤት ሳደርሳት እንደዚህ ያለ ነገር ውስጥ፣ ስራ ቦታዬ ላለመግባት ወስኜ እንደነበር፣
ነገር ግን፣ የእርሷ ውበት ከምቆጣጠረው በላይ እንደሆነብኝና የሆነው ድንገት እንደሆነ ነገርኳት፡፡ ስራችን ላይ ተፅዕኖ እንዳይኖር፣ ሰው እንዳያውቅ ጠየኳት፣፥ ግቢ ውስጥ እንድንጠነቀቅ አሳሰብኳት፡፡ እርሷም እንደዛ እንደማትፈልግና እንደምትጠነቀቅ አረጋገጠችልኝ፡፡
ህይወት ቀና ሆነችልኝ፡፡ በጣም ደስተኛ ሆንኩ፡፡ ስራዎችን በሚገባ አቅዳለሁ! አፈፃፀማቸውን እከታተላለሁ! ለአለቃዬ ሁሉንም በግዜው ሪፖርት አደርጋለሁ፡፡ ሁሉም በስራዬ ደስተኛ ሆኑ፡፡ በተለይ
አለቃዬ ያበረታቱኛል። በውስጤ ብዙ እምቅ አቅም እንዳለ ይነግሩኛል፡፡
ስለ ስራ ልምዳቸው፣ ከፍተኛ ትምህርት ውጪ ሃገር ሄደው ስለመከታተላቸው፣ እኔም እንደዚህ ጠንክሬ ከሰራሁ ትልቅ ደረጃ እንደምደርስ በተገናኘን ቁጥር ይነግሩኛል፡፡ ብዙ ስራተኛ ይፈራቸዋል፡፡
ቁጡና ሃይለኛ ናቸው ይላሉ፡፡ በተለይ ደግሞ ድርጅቱ የዘመዳቸው ስለሆነ፣ ፈላጭ ቆራጭ ናቸው ይላሉ፡፡ በዚህም፣ ሰራተኛው እንዳሻው ብሎ የቅፅል ስም አውጥቶላቸዋል፡፡ እኔ ግን ነገሮችን በፍጥነት የመረዳት አቅማቸው፣ ልምዳቸውን ለማካፈልና ሰውን ለማሳደግ ያላቸው ቀናነትን ስመለከት እያደር በጣም እንዳደንቃቸው አድርገውኛል፡፡
ዛሬ ቅዳሜ ነው፡፡ ቅዳሜ ብዙ ስራ የለም፡፡ ስራተኞች እንደገቡ ካረጋገጥኩና ምርት በሚጠበቀው እየተመረተ እንደሆነ ካየሁ በኋላ፣ሰዓት እስኪደርስልኝ በየቢሮው እየተንቀሳቀስኩ ምልከታ አደርጋለሁ፡፡
ጨርሼ ቢሮዬ እንደተቀመጥኩ፣ ማሂ እንደተለመደው መጥታ ሸኘኝ አለችኝ፡፡ ለመውጣት እየተዘጋጀን፣ ሳሚ በሩን ከፍቶ ገባ፡፡ ሳሚ የሂሳብ ክፍል ሃላፊ ነው፡፡ ረጅምና ግዙፍ ተክለ ሰውነት ያለው ሲሆን፣ በባህሪው ሳቂታና ብቻውን መሆን ሚከብደው አይነት ሰው፡፡ ሰላምታ
ከተለዋወጥን በኋላ፣
“ዛሬ ትልቅ ደስታ አለኝ፡፡ ምን እንደሆነ አልናገርም፡፡ ግን የደስደ
ሱን ልጋብዛችሁ ፍቃደኛ ነኝ፡፡ ፈቃደኛ ናችሁ?” ፈገግ ብሎ
ቁልቁል እየተመለከተ ጠየቀን፡፡
ተገኝቶ ነው?፣ ያውም በደስታ ነዋ!” አልኩት፡፡
በሉ እንውጣ!”
“እንዴ ቆይ እኔንም ጠብቁኛ፣ ቢሮ ዘግቼ ልምጣ?” ማሂ መልስ ሳትጠብቅ ወጥታ ሄደች፡፡ ቢሮ ቆልፈን፣ ማሂን ለመጠበቅ ቀስ ብለን እየተራመድን፣ ከነጩ
ህንፃ በር ላይ. ግርማና ቤቲ ቆመው አየናቸው፡፡ ቤቲ ሂሳብ ክፍል ምትሰራ የግቢያችን አንዷ ቆንጆ ነች፡፡ ለሴት ረጅም የሚባል ቁመና ያላት፣ ቀይ፣ ተግባቢና ደፋር ልጅ ናት፡፡ ትውልዷም እድገቷም አዳማ ነው፡፡ አሁንም ከቤተሰቧ ጋር ትኖራለች፡፡ ጥርሷ እንዳብዛኛው ያገሩ ሰው፣ የበዛ ባይሆንም፣ ለፈገግታዋ ውበት የሆነ ትንሽ ብልዝ አለባት፡፡በግሩፓችን፣ ወርቃማው ፈገግታ ጎልደን ስማይል እንላታለን፡፡ ማታ ላይ በስልክ አልፎ አልፎ አወራታለሁ፡፡ መስሪያ ቤት ግን ከስራ ውጪ ብዙም አላዋራትም፡፡ እርሷ ግን፣ ስትፈልግ ቢሮዬ ድረስ ሰተት ብላ
ትመጣለች፡፡ ከሳሚ ጋር አንድ ቢሮ ናቸው፡፡ ክፍላቸው ብዙ ሰራተኛ
ስላለና ስለማይመቸው፣ እኔ ቢሮ ሲያገኛት እወድሻለሁ፣ ካልሳምኩሽ
እያለ ይላፋታል፡፡ ከስራ በኋላ ካልጋበዝኩሽ ብሎ ደጋግሞ ሲጠይቃትም ሰምቻለሁ፡፡ እሺ አትለውም፡፡ እኔ ደግሞ፣ እንከኗ ይሄ ነው ባልልም፣ ስምጥ ብላ አልገባችልኝም፡፡ የሆነ ሚጎረብጥ ነገር እንዳላት ይሰማኛል፡፡ ዛሬ ቤቲ አብራን ከወጣች የሳሚ የደስ ደስ እርሷ ናት፤ ብዬ አሰብኩ፡፡
“እንውጣ፣ ኮተት እንዳይበዛ፡፡” አለ ሳሚ ወደ መኪናዋ እየሄደ የመኪናውን የሪሞት ቁልፍ ተጭኖት፡ የግቢው መኪና ማቆሚያ ውስጥ ተደርድረው ከቆሙት መኪኖች ጥቁሯ ቪታራ፣ ዋይ ዋይ ማለት
ጅመረች፡፡
“አንድ ሰው ካንተ ጋር ይሁና?” አለኝ ሳሚ፣ የከፈተውን የጋቢናውን በር ተደግፎ፡፡
“እሺ!”
ወዲያው ማሂ መጥታ መኪናዬ ውስጥ ገባች፡፡ የተለመደው ስጋ ቤት ስደርስ፣ ሳሚ እያቆመ ነው፡፡ አጠገቡ ሄጄ አቆምኩ፡፡ ስጋ ቤቱ እንደተለመደው ደርቷል፡፡ ባለቤቱ ገና እንዳየን ሚያብለጨልጭ መላጣውን እያሻሽ ወደ ጓሮ ይዞን ገባ፡፡
“ማነህ፣ ና እስቲ! እዚህ ጋር ሁለት ወንበር ጨምርላቸው፡፡”ጮኸ፡፡ ሳሚ ለቤቲ ከጎኑ ወንበር አስተካክሎ፣ ጎንበስ ብሎ እንድትቀመጥ ጋበዛት፡፡ ተቀመጠች፡፡ ግርማ ከቤቲ ጎን ተቀመጠ፡፡ ማሂ ቀጠለች፣ እኔ ክቡን ለመሙላት በማሂና በሳሚ መሃከል ወንበር አስተካክዬ
ተቀመጥኩ፡፡
“ጠፍታችኋል፣ በሰላም ነው?” ባለቤቱ የግሩፑን መሪ ሳሚን ጠየቀው፡፡ ሳሚ ጭር ሲል ማይወድ፣ ነገር ቶሎ ሚረብሽውና ነገርን እንደጦር ሚሸሽ ነው፡፡ ወሬ ሚያቋርጠውን ሰው አይወድም፡፡እንደሚፈልገው ስለምሆንለት፣ ከኔ ጋር መሆን የበለጠ ነፃነት ይሰጠዋል፡፡ ጨዋታ ደምቆ ደስ ካለው ደግሞ፣ ድንገት ተነስቶ ጋባዥ
ነኝ ማለት ይወዳል።
“ምን እንጠፋለን፣ ቅዳሜ መጥተን አልነበር?”
“እሺ ስንት ልዘዝላችሁ? ሁለት
ላድርገው...?”
“አድርገው፡፡”
“የሚጠጣ፣ ያ የተለመደውን?”
“እሺ፡፡ ደግሞ ከረሜላ ላክልን፤ አሪፍ ይሁን ሳሚ የተለመደውን ትዕዛዙን አስከተለ፡፡
ሰውዬው እንደሄደ፣ ጫጫታው
መድረኩን ተረከቡት፡፡ የጀማው ድርሻ የነሱ ሃሳብ ላይ መጨመር፣ አስተያየት መስጠት ወይም መሳቅ ብቻ ነው፡፡ ሚያስቁ ትዝታቸውን፣ ቀልዶችን እያወሩ ይበሻሽቃሉ፤ ያስቁናል፡፡ ከረሜላው ከአዋሽ ተከሽኖ ጋር መጣ፡፡ ጥብሱ ተከተለ፡፡ መጠጡ በፍጥነት ያልቃል፡፡ ከሁለተኛው በኋላ፣ ማን እንደሚያዝ እንኳ አይታወቅም፡፡ ቦታው ሰወር ያለ
በመሆኑ፣ እንደፈለግን ለመንጫጫት ተመችቶናል፡፡ አንዱ ወሬ ሲያልቅ
ሌላ ይቀየራል፡፡ ያኛውስ፣ እንትን” እያሉ ሳሚና ማሂ ይሽቀዳደማሉ።አንዳንዴ አልደማመጥ ሲሉ፣ ማሂ ወደኔ ትዞራለች፡፡ ሳሚ አጠገቡ ላለችው ቤቲ ያወራል። መልሰው በጋራ አንድ ወሬ ይጀምራሉ፡፡ አሁን የቤቲም የግርማም ድምፅ ጎልቶ መሰማት ጀምሯል፡፡
“ሳሚ፣ ሳሚ፣ አንተ...” ማሂ ጮኸች፡፡
“ወይዬ፣ቆንጆ”
ነገ ሶደሬ እንሂድ?”
“ዛሬ ካልደከምን፣ አይተን እንደሙዳችን።”
“እንሂድ በናትህ ... ኪ.ኪ.ኪ...”
“ምንድን ነው? መረጫጨት ነው እንዴ?”
“እንደፈራሁት አይደለም ናፍቆኛል...፡፡ ኪ.ኪ.ኪ...” ማውራት እስኪያቅታት ትስቅ ጀመር፡፡ እሱም አብሯት መንከትከት
ጀመረ።
“እንዴ ንገሩን እና እኛም አብረን እንሳቅ እንጂ..ሃይ!” በመሃል ገባሁ፡፡
“ይኸውልህ ያቡ፣ ባለፈው ከስራ ስንወጣ ሶደሬ ካልሄድን ብሎኝ ሄድን፡፡ ከዛ ካልዋኘሁ ብሎ ተከፍሎ ሚዋኝበት ስንሄድ፣ ስው ሚባል የለም፡፡ እዋኛለሁ ብሎ ገባ፡፡ ከዛ ወዲያው ብቅ ጥልቅ መጫወት አይጀምርም...፡፡ ኪ.ኪ.ኪ..
ደንግጬ እጄን ብሰጠው፣ ብጠራው
ሊሰማኝ ነው...፡፡ ከዛ ኡ...ኡታዬን አስነካሁታ፡፡ ኪ.ኪ.ኪ...ሁላችንም ተከትለናት እንስቃለን፣ እሱም አብሮን ይስቃል...።
“በናትሽ ከዛስ?”
“ከዛማ የሆኑ ሰዎች መጥተው አወጡት፡፡ ኪ.ኪ.ኪ...። አቤት ያስመለሰው ውሃ ብዛቱ... ኪ...ኪ...ኪ... ከመቼው ያን ሁላ ውሃ እንደጠጣ... ኪ.ኪ.ኪ...፣ ደግሞኮ ሲገባ፣ ገንዳው ቆሽሿል ምናምን ሲለኝ፣ ሊጠጣ እንደሚገባ እኔ መች ገባኝ... ኪ.ኪ.ኪ...” ማውራት እሰኪያቅታት ትስቃለች፡፡ ሳሚም ይስቃል፣ እኛም ተከትለን
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ(MD)
በመጨረሻም ተስማማች፣ እኔ ጋር
አደረች፡፡ በተከፈተልኝ በር ወስኜ መግባት እንዳልከበደኝ፣ አለባበሷና የወይኑ ስሜት ተደማምሮ፣ በድንገት ሰተት ብዬ ገባሁ፡፡ የመጀመሪያ ቀን አይቻት ስደነግጥ እንዲህ በቀላሉ ማገኛት፣ እኔ ላይ እንዲህ ፍላጎት አሳይታ እሺ ምትላኝ አልመሰለኝም ነበር፡፡ በጥዋት ወደ ቤት ሳደርሳት እንደዚህ ያለ ነገር ውስጥ፣ ስራ ቦታዬ ላለመግባት ወስኜ እንደነበር፣
ነገር ግን፣ የእርሷ ውበት ከምቆጣጠረው በላይ እንደሆነብኝና የሆነው ድንገት እንደሆነ ነገርኳት፡፡ ስራችን ላይ ተፅዕኖ እንዳይኖር፣ ሰው እንዳያውቅ ጠየኳት፣፥ ግቢ ውስጥ እንድንጠነቀቅ አሳሰብኳት፡፡ እርሷም እንደዛ እንደማትፈልግና እንደምትጠነቀቅ አረጋገጠችልኝ፡፡
ህይወት ቀና ሆነችልኝ፡፡ በጣም ደስተኛ ሆንኩ፡፡ ስራዎችን በሚገባ አቅዳለሁ! አፈፃፀማቸውን እከታተላለሁ! ለአለቃዬ ሁሉንም በግዜው ሪፖርት አደርጋለሁ፡፡ ሁሉም በስራዬ ደስተኛ ሆኑ፡፡ በተለይ
አለቃዬ ያበረታቱኛል። በውስጤ ብዙ እምቅ አቅም እንዳለ ይነግሩኛል፡፡
ስለ ስራ ልምዳቸው፣ ከፍተኛ ትምህርት ውጪ ሃገር ሄደው ስለመከታተላቸው፣ እኔም እንደዚህ ጠንክሬ ከሰራሁ ትልቅ ደረጃ እንደምደርስ በተገናኘን ቁጥር ይነግሩኛል፡፡ ብዙ ስራተኛ ይፈራቸዋል፡፡
ቁጡና ሃይለኛ ናቸው ይላሉ፡፡ በተለይ ደግሞ ድርጅቱ የዘመዳቸው ስለሆነ፣ ፈላጭ ቆራጭ ናቸው ይላሉ፡፡ በዚህም፣ ሰራተኛው እንዳሻው ብሎ የቅፅል ስም አውጥቶላቸዋል፡፡ እኔ ግን ነገሮችን በፍጥነት የመረዳት አቅማቸው፣ ልምዳቸውን ለማካፈልና ሰውን ለማሳደግ ያላቸው ቀናነትን ስመለከት እያደር በጣም እንዳደንቃቸው አድርገውኛል፡፡
ዛሬ ቅዳሜ ነው፡፡ ቅዳሜ ብዙ ስራ የለም፡፡ ስራተኞች እንደገቡ ካረጋገጥኩና ምርት በሚጠበቀው እየተመረተ እንደሆነ ካየሁ በኋላ፣ሰዓት እስኪደርስልኝ በየቢሮው እየተንቀሳቀስኩ ምልከታ አደርጋለሁ፡፡
ጨርሼ ቢሮዬ እንደተቀመጥኩ፣ ማሂ እንደተለመደው መጥታ ሸኘኝ አለችኝ፡፡ ለመውጣት እየተዘጋጀን፣ ሳሚ በሩን ከፍቶ ገባ፡፡ ሳሚ የሂሳብ ክፍል ሃላፊ ነው፡፡ ረጅምና ግዙፍ ተክለ ሰውነት ያለው ሲሆን፣ በባህሪው ሳቂታና ብቻውን መሆን ሚከብደው አይነት ሰው፡፡ ሰላምታ
ከተለዋወጥን በኋላ፣
“ዛሬ ትልቅ ደስታ አለኝ፡፡ ምን እንደሆነ አልናገርም፡፡ ግን የደስደ
ሱን ልጋብዛችሁ ፍቃደኛ ነኝ፡፡ ፈቃደኛ ናችሁ?” ፈገግ ብሎ
ቁልቁል እየተመለከተ ጠየቀን፡፡
ተገኝቶ ነው?፣ ያውም በደስታ ነዋ!” አልኩት፡፡
በሉ እንውጣ!”
“እንዴ ቆይ እኔንም ጠብቁኛ፣ ቢሮ ዘግቼ ልምጣ?” ማሂ መልስ ሳትጠብቅ ወጥታ ሄደች፡፡ ቢሮ ቆልፈን፣ ማሂን ለመጠበቅ ቀስ ብለን እየተራመድን፣ ከነጩ
ህንፃ በር ላይ. ግርማና ቤቲ ቆመው አየናቸው፡፡ ቤቲ ሂሳብ ክፍል ምትሰራ የግቢያችን አንዷ ቆንጆ ነች፡፡ ለሴት ረጅም የሚባል ቁመና ያላት፣ ቀይ፣ ተግባቢና ደፋር ልጅ ናት፡፡ ትውልዷም እድገቷም አዳማ ነው፡፡ አሁንም ከቤተሰቧ ጋር ትኖራለች፡፡ ጥርሷ እንዳብዛኛው ያገሩ ሰው፣ የበዛ ባይሆንም፣ ለፈገግታዋ ውበት የሆነ ትንሽ ብልዝ አለባት፡፡በግሩፓችን፣ ወርቃማው ፈገግታ ጎልደን ስማይል እንላታለን፡፡ ማታ ላይ በስልክ አልፎ አልፎ አወራታለሁ፡፡ መስሪያ ቤት ግን ከስራ ውጪ ብዙም አላዋራትም፡፡ እርሷ ግን፣ ስትፈልግ ቢሮዬ ድረስ ሰተት ብላ
ትመጣለች፡፡ ከሳሚ ጋር አንድ ቢሮ ናቸው፡፡ ክፍላቸው ብዙ ሰራተኛ
ስላለና ስለማይመቸው፣ እኔ ቢሮ ሲያገኛት እወድሻለሁ፣ ካልሳምኩሽ
እያለ ይላፋታል፡፡ ከስራ በኋላ ካልጋበዝኩሽ ብሎ ደጋግሞ ሲጠይቃትም ሰምቻለሁ፡፡ እሺ አትለውም፡፡ እኔ ደግሞ፣ እንከኗ ይሄ ነው ባልልም፣ ስምጥ ብላ አልገባችልኝም፡፡ የሆነ ሚጎረብጥ ነገር እንዳላት ይሰማኛል፡፡ ዛሬ ቤቲ አብራን ከወጣች የሳሚ የደስ ደስ እርሷ ናት፤ ብዬ አሰብኩ፡፡
“እንውጣ፣ ኮተት እንዳይበዛ፡፡” አለ ሳሚ ወደ መኪናዋ እየሄደ የመኪናውን የሪሞት ቁልፍ ተጭኖት፡ የግቢው መኪና ማቆሚያ ውስጥ ተደርድረው ከቆሙት መኪኖች ጥቁሯ ቪታራ፣ ዋይ ዋይ ማለት
ጅመረች፡፡
“አንድ ሰው ካንተ ጋር ይሁና?” አለኝ ሳሚ፣ የከፈተውን የጋቢናውን በር ተደግፎ፡፡
“እሺ!”
ወዲያው ማሂ መጥታ መኪናዬ ውስጥ ገባች፡፡ የተለመደው ስጋ ቤት ስደርስ፣ ሳሚ እያቆመ ነው፡፡ አጠገቡ ሄጄ አቆምኩ፡፡ ስጋ ቤቱ እንደተለመደው ደርቷል፡፡ ባለቤቱ ገና እንዳየን ሚያብለጨልጭ መላጣውን እያሻሽ ወደ ጓሮ ይዞን ገባ፡፡
“ማነህ፣ ና እስቲ! እዚህ ጋር ሁለት ወንበር ጨምርላቸው፡፡”ጮኸ፡፡ ሳሚ ለቤቲ ከጎኑ ወንበር አስተካክሎ፣ ጎንበስ ብሎ እንድትቀመጥ ጋበዛት፡፡ ተቀመጠች፡፡ ግርማ ከቤቲ ጎን ተቀመጠ፡፡ ማሂ ቀጠለች፣ እኔ ክቡን ለመሙላት በማሂና በሳሚ መሃከል ወንበር አስተካክዬ
ተቀመጥኩ፡፡
“ጠፍታችኋል፣ በሰላም ነው?” ባለቤቱ የግሩፑን መሪ ሳሚን ጠየቀው፡፡ ሳሚ ጭር ሲል ማይወድ፣ ነገር ቶሎ ሚረብሽውና ነገርን እንደጦር ሚሸሽ ነው፡፡ ወሬ ሚያቋርጠውን ሰው አይወድም፡፡እንደሚፈልገው ስለምሆንለት፣ ከኔ ጋር መሆን የበለጠ ነፃነት ይሰጠዋል፡፡ ጨዋታ ደምቆ ደስ ካለው ደግሞ፣ ድንገት ተነስቶ ጋባዥ
ነኝ ማለት ይወዳል።
“ምን እንጠፋለን፣ ቅዳሜ መጥተን አልነበር?”
“እሺ ስንት ልዘዝላችሁ? ሁለት
ላድርገው...?”
“አድርገው፡፡”
“የሚጠጣ፣ ያ የተለመደውን?”
“እሺ፡፡ ደግሞ ከረሜላ ላክልን፤ አሪፍ ይሁን ሳሚ የተለመደውን ትዕዛዙን አስከተለ፡፡
ሰውዬው እንደሄደ፣ ጫጫታው
መድረኩን ተረከቡት፡፡ የጀማው ድርሻ የነሱ ሃሳብ ላይ መጨመር፣ አስተያየት መስጠት ወይም መሳቅ ብቻ ነው፡፡ ሚያስቁ ትዝታቸውን፣ ቀልዶችን እያወሩ ይበሻሽቃሉ፤ ያስቁናል፡፡ ከረሜላው ከአዋሽ ተከሽኖ ጋር መጣ፡፡ ጥብሱ ተከተለ፡፡ መጠጡ በፍጥነት ያልቃል፡፡ ከሁለተኛው በኋላ፣ ማን እንደሚያዝ እንኳ አይታወቅም፡፡ ቦታው ሰወር ያለ
በመሆኑ፣ እንደፈለግን ለመንጫጫት ተመችቶናል፡፡ አንዱ ወሬ ሲያልቅ
ሌላ ይቀየራል፡፡ ያኛውስ፣ እንትን” እያሉ ሳሚና ማሂ ይሽቀዳደማሉ።አንዳንዴ አልደማመጥ ሲሉ፣ ማሂ ወደኔ ትዞራለች፡፡ ሳሚ አጠገቡ ላለችው ቤቲ ያወራል። መልሰው በጋራ አንድ ወሬ ይጀምራሉ፡፡ አሁን የቤቲም የግርማም ድምፅ ጎልቶ መሰማት ጀምሯል፡፡
“ሳሚ፣ ሳሚ፣ አንተ...” ማሂ ጮኸች፡፡
“ወይዬ፣ቆንጆ”
ነገ ሶደሬ እንሂድ?”
“ዛሬ ካልደከምን፣ አይተን እንደሙዳችን።”
“እንሂድ በናትህ ... ኪ.ኪ.ኪ...”
“ምንድን ነው? መረጫጨት ነው እንዴ?”
“እንደፈራሁት አይደለም ናፍቆኛል...፡፡ ኪ.ኪ.ኪ...” ማውራት እስኪያቅታት ትስቅ ጀመር፡፡ እሱም አብሯት መንከትከት
ጀመረ።
“እንዴ ንገሩን እና እኛም አብረን እንሳቅ እንጂ..ሃይ!” በመሃል ገባሁ፡፡
“ይኸውልህ ያቡ፣ ባለፈው ከስራ ስንወጣ ሶደሬ ካልሄድን ብሎኝ ሄድን፡፡ ከዛ ካልዋኘሁ ብሎ ተከፍሎ ሚዋኝበት ስንሄድ፣ ስው ሚባል የለም፡፡ እዋኛለሁ ብሎ ገባ፡፡ ከዛ ወዲያው ብቅ ጥልቅ መጫወት አይጀምርም...፡፡ ኪ.ኪ.ኪ..
ደንግጬ እጄን ብሰጠው፣ ብጠራው
ሊሰማኝ ነው...፡፡ ከዛ ኡ...ኡታዬን አስነካሁታ፡፡ ኪ.ኪ.ኪ...ሁላችንም ተከትለናት እንስቃለን፣ እሱም አብሮን ይስቃል...።
“በናትሽ ከዛስ?”
“ከዛማ የሆኑ ሰዎች መጥተው አወጡት፡፡ ኪ.ኪ.ኪ...። አቤት ያስመለሰው ውሃ ብዛቱ... ኪ...ኪ...ኪ... ከመቼው ያን ሁላ ውሃ እንደጠጣ... ኪ.ኪ.ኪ...፣ ደግሞኮ ሲገባ፣ ገንዳው ቆሽሿል ምናምን ሲለኝ፣ ሊጠጣ እንደሚገባ እኔ መች ገባኝ... ኪ.ኪ.ኪ...” ማውራት እሰኪያቅታት ትስቃለች፡፡ ሳሚም ይስቃል፣ እኛም ተከትለን
👍6👏2🔥1
እንስቃለን፡፡ወሬውን ሊያስቀይራት ቢልም፣ አላቆም ስትለው አስተናጋጁን ድንገት፣
“ና እስቲ ሚጠጣ ጨምርልን!” አለው፡፡
“ደግሞኮ፣ በጣም ያሳቀኝ፣ስንመለስ መኪና ውስጥ፣
ኪ......ኪ....ኪ...... እንዴት ነህ?' ስለው፣ “እንደፈራሁት አይደለም አይለኝም... ኪ.ኪ...ኪ...”
ካ..ካ..ካ... ከዛ በላይ፣ ምን ነበር የፈራው...?” እኔም መሃል ገባሁ፡፡
“እንደዛ የተንቀለቀለው፣ ውሃ ጠምቶት ነው ለካ ኪ.ኪ.ኪ. እንደዚህ እየተጫወትን ቤት ሳንቀይር መሸ፡፡ ሰዓቴ ከምሽቱ
ሶስት ሰዓት ይላል፡፡ ሁሉም ሞቅ ያለው ይመስላል፡፡ የሳሚ ግንባሩ ደም ስር ተወጣጥሯል፡፡ ፊቱ ወዝቷል፡፡ እንደዛ አየተሳሳቅን ድንገት ግርማና ቤቲ ይጨቃጨቃሉ። ሳሚ ጨዋታውን አቁሞ ሊያግባባቸው መሃል ገባ፡፡ ነገሩ ጭራሽ ጦዘ፡፡
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
“ና እስቲ ሚጠጣ ጨምርልን!” አለው፡፡
“ደግሞኮ፣ በጣም ያሳቀኝ፣ስንመለስ መኪና ውስጥ፣
ኪ......ኪ....ኪ...... እንዴት ነህ?' ስለው፣ “እንደፈራሁት አይደለም አይለኝም... ኪ.ኪ...ኪ...”
ካ..ካ..ካ... ከዛ በላይ፣ ምን ነበር የፈራው...?” እኔም መሃል ገባሁ፡፡
“እንደዛ የተንቀለቀለው፣ ውሃ ጠምቶት ነው ለካ ኪ.ኪ.ኪ. እንደዚህ እየተጫወትን ቤት ሳንቀይር መሸ፡፡ ሰዓቴ ከምሽቱ
ሶስት ሰዓት ይላል፡፡ ሁሉም ሞቅ ያለው ይመስላል፡፡ የሳሚ ግንባሩ ደም ስር ተወጣጥሯል፡፡ ፊቱ ወዝቷል፡፡ እንደዛ አየተሳሳቅን ድንገት ግርማና ቤቲ ይጨቃጨቃሉ። ሳሚ ጨዋታውን አቁሞ ሊያግባባቸው መሃል ገባ፡፡ ነገሩ ጭራሽ ጦዘ፡፡
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1