ከእንቅልፌ ባንኜ ነቃሁ እና ድንኳኔ
ውስጥ እንዳለሁ መተኮስ ጀመርኩ ጥይቶቼን እስከምጨርስ ለስላሳ ዙር ተኮስኩ። መቶ አለቃ እና አስር አለቃ መጥተው ወደ ውጭ ወሰዱኝ። አልቦኝ ነበር፤ ፊቴ ላይ ውሃ ከደፉብኝ በኋላ
ክኒን ስጡኝ። ሙሉ ለሊቱን ቁሜ አደርኩ። ለሳምንት ያህል መተኛት አልቻልኩም። ለተጨማሪ ሁለት ቀናት ለውጊያ
ወጥተን ነበር፤ መሳሪያየን ለመተኮስ አልተቸገርኩም::
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ውስጥ እንዳለሁ መተኮስ ጀመርኩ ጥይቶቼን እስከምጨርስ ለስላሳ ዙር ተኮስኩ። መቶ አለቃ እና አስር አለቃ መጥተው ወደ ውጭ ወሰዱኝ። አልቦኝ ነበር፤ ፊቴ ላይ ውሃ ከደፉብኝ በኋላ
ክኒን ስጡኝ። ሙሉ ለሊቱን ቁሜ አደርኩ። ለሳምንት ያህል መተኛት አልቻልኩም። ለተጨማሪ ሁለት ቀናት ለውጊያ
ወጥተን ነበር፤ መሳሪያየን ለመተኮስ አልተቸገርኩም::
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
😱1
#ዐዲስ_ገጽ
ያላለምኩት
ያልጠየኩት ኾነ !
ልቤ ጥበብ ገባው . . ፤
ምስጢርን ዐወቀ
ዐውቆ ተራቀቀ
ተራቆም ራቀ።
ሐሳቡን አፍታታ ፤ ሐሳቡን አናኘው
ጥያቄው ምሶ ፣ ምላሹን አገኘው።
በሐሳብ ተሞልቶ
በሐሳብ ተመርቶ
መጠየቅ ጀመረ ፤
ያልተፈቀደውን
የተደበቀውን
እየመረመረ።
እየመረመረ፤
በከፍታ ጕዞ . . .
ሽቅብ ተምዘግዝጎ ከኅዋው ላይ ዋለ
ከእርሱ ተገናኘ ከዚያም ይኼን አለ።
ጠቢቡ ሠለሞን . . .
“ከፀሓይዋ በታች ዐዲስ ነገር የለም ! "
ብሎ በመናገር .
የተሰጠው ኹሉ በከንቱ ከኾነ ፣
ከታችኛው ሳይኾን . . .
ከከፍታው ላይ ነው ፤ ሕልሙ የመከነ።
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
ያላለምኩት
ያልጠየኩት ኾነ !
ልቤ ጥበብ ገባው . . ፤
ምስጢርን ዐወቀ
ዐውቆ ተራቀቀ
ተራቆም ራቀ።
ሐሳቡን አፍታታ ፤ ሐሳቡን አናኘው
ጥያቄው ምሶ ፣ ምላሹን አገኘው።
በሐሳብ ተሞልቶ
በሐሳብ ተመርቶ
መጠየቅ ጀመረ ፤
ያልተፈቀደውን
የተደበቀውን
እየመረመረ።
እየመረመረ፤
በከፍታ ጕዞ . . .
ሽቅብ ተምዘግዝጎ ከኅዋው ላይ ዋለ
ከእርሱ ተገናኘ ከዚያም ይኼን አለ።
ጠቢቡ ሠለሞን . . .
“ከፀሓይዋ በታች ዐዲስ ነገር የለም ! "
ብሎ በመናገር .
የተሰጠው ኹሉ በከንቱ ከኾነ ፣
ከታችኛው ሳይኾን . . .
ከከፍታው ላይ ነው ፤ ሕልሙ የመከነ።
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
👍1
#ውሉድ_ወወላድ
የወለደች ኹሉ . . .
እናት አትባልም! ግብሯ ካልተለየ ፤
የተወለደ ልጅ . . .
አይባልም ጧሪ!ምግባሩን ካለየ።
ዘር ስላካፈለ . . .
የአባት መኾን ክብር በከንቱ አይሰጥም!
ከልጅ ስም ቀጥሎ ስሙ አይቀመጥም!
እፍኝትን እይዋት .
እናት ትሞታለች ፣ ትውልድ ለማስቀጠል
አባትም ይሠዋል ፣በፍትወት መቃጠል።
አንበሳም ደቦሉን .
በጊዜው ካልቀጣ ንግሥናው ይቀማል ፤
የልጅነት ሥሥት ፣
የአባትነት ድርሻ ለክብር ይወድማል።
አዎ !
እናት ክብሯን ይዛ፣
ልጅ ግብሩን ተላብሶ ፣
አባት በስም ነግሦ፣
ካልተነጻጸረ፣
የመዳን ምሳሌው ትንቢቱ ተሻረ።
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
የወለደች ኹሉ . . .
እናት አትባልም! ግብሯ ካልተለየ ፤
የተወለደ ልጅ . . .
አይባልም ጧሪ!ምግባሩን ካለየ።
ዘር ስላካፈለ . . .
የአባት መኾን ክብር በከንቱ አይሰጥም!
ከልጅ ስም ቀጥሎ ስሙ አይቀመጥም!
እፍኝትን እይዋት .
እናት ትሞታለች ፣ ትውልድ ለማስቀጠል
አባትም ይሠዋል ፣በፍትወት መቃጠል።
አንበሳም ደቦሉን .
በጊዜው ካልቀጣ ንግሥናው ይቀማል ፤
የልጅነት ሥሥት ፣
የአባትነት ድርሻ ለክብር ይወድማል።
አዎ !
እናት ክብሯን ይዛ፣
ልጅ ግብሩን ተላብሶ ፣
አባት በስም ነግሦ፣
ካልተነጻጸረ፣
የመዳን ምሳሌው ትንቢቱ ተሻረ።
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#የመኖር_ልኬ
ሰይጣን ከፈጣሪ እንዴት ይፏከራል?
እግዜርስ ከሰው ጋር እንዴት ይማከራል?
ድንቢጥ ሐሳብ ይዞ ከሰማይ ጋር መዋጋት
ደመና ላይ ምሎ ነፋስን መዘንጋት።
መርከብ ሳያበጁ መልሕቅ መወርወር
ከውቅያኖስ ጠልቆ ከውሃ መሰወር።
ጭላንጭሏ ኩራዝ ፀሓይን ረስታ
ጣራ አልባ ጎጆዋ ዝናብ ተመኝታ
ከማይችሉት መግጠም ከማይደርሱት ቦታ።
ውስጤ እንደዚህ ነው! የሚያግደረድረው
ሐሳቤ እንደዚህ ነው! የሚወዳደረው።
ስሜቴ ከልቤ እየተደበቀ
ነፍሴ ከምኞቴ እየተሳበቀ ፣
(ልቤ ትቢያ ቀረ . . .!)
ሚዛኑን ረስቶ እየተመዘነ
መመዘኛ ስቶ እየተተመነ ፣
ከማያሸንፈው እየተጋጠመ
የሽንፈቱን ጕዞ እየደጋገመ ፣
እየደጋገመ እየደጋገመ . . .
እያልጎመጎመ . . .!
ይኸው አለኹ አለ. .!
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
ሰይጣን ከፈጣሪ እንዴት ይፏከራል?
እግዜርስ ከሰው ጋር እንዴት ይማከራል?
ድንቢጥ ሐሳብ ይዞ ከሰማይ ጋር መዋጋት
ደመና ላይ ምሎ ነፋስን መዘንጋት።
መርከብ ሳያበጁ መልሕቅ መወርወር
ከውቅያኖስ ጠልቆ ከውሃ መሰወር።
ጭላንጭሏ ኩራዝ ፀሓይን ረስታ
ጣራ አልባ ጎጆዋ ዝናብ ተመኝታ
ከማይችሉት መግጠም ከማይደርሱት ቦታ።
ውስጤ እንደዚህ ነው! የሚያግደረድረው
ሐሳቤ እንደዚህ ነው! የሚወዳደረው።
ስሜቴ ከልቤ እየተደበቀ
ነፍሴ ከምኞቴ እየተሳበቀ ፣
(ልቤ ትቢያ ቀረ . . .!)
ሚዛኑን ረስቶ እየተመዘነ
መመዘኛ ስቶ እየተተመነ ፣
ከማያሸንፈው እየተጋጠመ
የሽንፈቱን ጕዞ እየደጋገመ ፣
እየደጋገመ እየደጋገመ . . .
እያልጎመጎመ . . .!
ይኸው አለኹ አለ. .!
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
👍1
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_አስራ_ሁለት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
ቀኖቼን በወታደራዊ ስራዎች ተጠምጄ ባሳለፍኩ ቁጥር የራስ ምታቴ እየተሻለኝ መጣ፡፡ ቀን ቀን ኳስ መጫወት ትቼ ጥበቃ
ላይ እሰማራለሁ። ነጩን ክኒን በብዛት አዘውትሬ እወስድ ነበር።
ክኒኖቹ ሱስ ሁነውብኛል። ብዙ ኃይል ይሰጡኛል። መጀመሪያ አብዝቼ የወሰድኩ ቀን በጣም አልቦኝ ሁሉንም ልብሶቼን አውልቄ ነበር። ሰውነቴ ይንቀጠቀጣል፤ ዕይታየ ደበዘዘ ብዥታ
ለደቂቃዎች ያህል መስማትም አልቻልኩም። ያለ ምንም ስራ
መንደሩን እዞረዋለሁ፤ እረፍት የለኝም ብዙ ኃይል ይሰማኛል ነገር ግን ደንዝዣለሁ ስሜት አይሰማኝም፡፡ ክኒኑን አብዝቼ
መውሰዴን ቀጠልኩ።ምንም ነገር አይሰማኝም ብዙ ኃይል ከማግኘት እና ለሳምንት እንቅልፍ ካለመተኛት በስተቀር። ማታ ማታ ፊልም እናያለን። የጦርነት ፊልሞች፥ራምቦ፣ ፈርስት ብለድ፣ ራምቦ ሁለት፣ ኮማንዶ እና ሌሎች በጄነሬተር ወይም በመኪና ባትሪ በመታገዘ እንመለከት ነበር። ሁላችንም እንደ
ራምቦ መሆን እንፈልግ ነበር። እሱ ያደረጋቸውን እንቅስቃሴዎች ለመተግበር እንጓጓ ነበር።
ምግብ፣ መድሃኒት፣ ጥይቶች እና ጋዝ እያለቀብን ሲመጣ በከተማ፣ በገጠር መንደሮች እና በጫካ ውስጥ የሚገኙ
በር የአማጺዎችን ካምፖችን መውረር ጀመርን። ያልታጠቁ ሰዎች የሚገኝባቸውን ሌሎች መንደሮችን በማጥቃት ወታደሮችን መለመልን፡፡
“መልካም ዜና ደርሶናል ከመልዕክተኞቻችን የተወሰኑ አማጺዎችን ለመግደል እና በመጀመሪያም የእኛ የሆነውን ቁሳቁሳቸውን ለመውሰድ ከአምስት ደቂቃ በኋላ ከዚህ እንቀሳቀሳለን” አለ መቶ አለቃ አዋጁን ሲነግር። ፊቱ ላይ ልበ ሙሉነት ይነበባል። ግንባራችን ላይ አረንጓዴ ጨርቅ አስረን
ነበር ታዳጊዎች ይመሩ ነበር። ምንም አይነት ካርታ ምንም አይነት ጥያቄም አልተነሳም:: ቀጣይ ትዕዛዝ እስከሚሰጠን ድረስ እንዲሁ መንገድ እንድንከተል ነበር የተነጋገርነው ሰርዲን ለመብላት እና ነጩን ክኒን ለመውሰድ ከቆምንበት ውጭ ለብዙ ሰአታት
ያለማቋረጥ ተጓዝን፡፡ ክኒኖቹ ብዙ ኃይል
ከመስጠታቸውም በላይ ደፋር አደረጉን፡፡ የሞት ሃሳብ በጭራሽ ወደ አዕምሮዬ አልመጣም፡፡ መግደል ግን ውሃ እንደመጠጣት ቀላል ሆነ። የመጀመሪያውን ሰው ስገድል ብቻ ልቤ ተነክቶ ነበር። ከዛ በኋላ ግን ምንም አይነት ሃዘን ፀፀት አልተሰማኝም::
ከበላን በኋላ መድሃኒቱን ወስደን አዋቂዎች ለተወሰነ ደቂቃ እረፍት እስኪወስዱ ዙሪያውን ለጥበቃ እንሰማራለን። ከ አልሃጂ ጋር ነበርኩ፡፡ የጥይት መያዣውን በፍጥነት መቀየርን
እየተወዳደርን ነበር።
“ቆይ አንድ ቀን ልክ እንደ ራምቦ ብቻየን አንድ ሙሉ መንደር እቆጣጠራለሁ” አል ሃጂ ፈገግ እያለ እቅዱን ነገረኝ።
ልክ እንደ ኮማንዶ ፊልም የራሴ ባዙቃ እንዲኖረኝ እፈልጋለሁ። ያምራል።” አልኩ እና አንድ ላይ ሳቅን፡፡
ወደ አማጺዎች ካምፕ ከመግባታችን በፊት መንገዳችን ቀይረን በጫካው ውስጥ በመጓዝ አሰሳ አናደርጋለን፡፡ ካምፑ ዕይታችን ውስጥ ከገባ በኋላሸ ከበባ እናደርግ እና የመቶ አለቃን ትዕዛዝ
እንጠብቃለን። አማጺዎች ከአንዱ ወደ አንዱ ይንቀሳቀሳሉ ፣ሌሎቹ ግድግዳ ተገድፈው ሲቀመጡ እንደእኛ ያሉ ታዳጊዎች ደግሞ ይጠብቃሉ:: አማጺዎችን ባየኋቸው ቁጥር ደሜ
ይፈላል፤ እናደዳለሁ። አማጺዎቹ ቤተሰቤን ያጣሁበትን መንደር አውድመው ካርታ የተጫወቱት ይመስሉኛል። ስለዚህ መቶ አለቃ ትዕዛዝ ሲሰጥ የቻልኩትን ያህል እተኩሳለሁ። ንዴቴ አይወጣልኝም! ከተኩስ በኋላ ወደ ካምፑ እንገባለን፡፡ የቆሰሉትን
እንገድላለን ፤ ቤት ውስጥ ገብተን ጋዝ፣ አደንዛዥ እፆች፣ ጫማ፣የእጅ ስዓቶች፣ ሩዝ፣ ዓሳ፣ ጨው እና ሌሎች ነገሮችን
እንሰበስባለን።ያልታጠቁ ሰዎችን (ሲቪል) ሰብስበን የዘረፍነውንእንዲሸከሙ እናደርጋለን።
“እኛ” መቶ አለቃ ወደ እኛ እየጠቆመ ” ልንጠብቃችሁ ነው እዚህ ያለነው። ምንም አይነት ጉዳት እንዳይደርስባችሁ የምንችለውን እናደርጋለን።” አለ ወደ ያልታጠቁት ሰዎች እየጠቆመ።
“የእኛ ስራ ጥብቅ ነው፤ ሃገራቸውን ለመጠበቅ ምንም አይነት መስዋዕትነት ለመክፈል የተዘጋጁ ጎበዝ ወታደሮችም
አሉን። እኛ እንደ አማጺዎች አይደለንም። እነዛ ነፍስ ገዳዮች ያለ ምንም ምክንያት ሰው ይገድላሉ፤ ሁሉንም ሰው በጅምላ
ይጨፈጭፋሉ። እኛ ግን የሃገራችንን ለመጠበቅ፤ አገራችን ከእነሱ ክፋት እና ጥፋት ለማዳን ስንል ብቻ እንገድላቸዋለን።ስለዚህ ለእነዚህ የሃገራችሁ ጠባቂዎች ክብር ስጡ” ብሎ መቶ አለቃ ረጂም ንግግር አደረገ። ንግግሩ ሁለት ዓላማ ነበረው።
አንዱ በሲቪሎች ስለ እኛ ጥሩ አመለካከት እንዲኖራቸው ማድረግ ሲሆን ሌላው ደግሞ የእኛን ሞራል መገንባት ነበር።ጠበንጃየን ይዤ ቁሜለሁ። ልዩ የመሆን ስሜት ተሰማኝ፣የተፈላጊነት ፤ አንድ ትልቅ እና ጥብቅ ነገር ተሳታፊ መሆን እና ከአሁን በኋላ ደግሞ ከማንም አልሸሽም።ሽጉጤ አለኝ አስር አለቃ ሁልጊዜ እንደሚለው “ ይሄ መሳሪያ በዚህ ጊዜ የሃይላችሁ ምንጭ ነው:: ይጠብቃችኋል! እንዴት መጠቀም እንዳለባችሁ ካወቃችሁ ደግሞ የምትፈልጉትን ሁሉ ይሰጣችኋል።
መቶ አለቃ ንግግሩን ለማድረግ ምን እንደገፋፋው አላስታውስም። ብዙ ነገሮች ያለ ምንም ምክንያት ወይም ማብራሪይ ይሰሩ ነበር። አንዳንዴ ፊልም እያየን መሐል ላይ ድንገት ለጦርነት እንድንቀሳቀስ እንጠየቃለን። ከስዓታት በኋላ እንዳልተፈጠረ ከማስታወቂያ በኋላ እንደተመለስ ፊልሙን ካቆምንበት
እንቀጥላለን። ሁሌም ውጊያ ላይ ነን ወይ የጦርነት ፊልም እየተመለክትን ነው ወይ ደግሞ አደንዛዥ ዕፅ እየወሰድን ነው።
ብቻችን የምንሆንበት የምናስብበት ምንም አይነት ጊዜ የለም::እርስበርሳችን ስናወራ የምናወራው ስለተመለከትነው የጦርነት ፊልሞች እና መቶ አለቃ፣ አስር አለቃ ወይም ከእኛ አንዳችን ስለፈፅምነው ጀብድ ብቻ ነበር። ከዛ ውጭ ሌላ አለም ያለ አይመስለንም ነበር።
ከመቶ አለቃ ንግግር በኋላ ተራ በተራ ምርኮኞችን በአሰቃቂ ሁኔታ ገደልን። አማጺዎችን ስንገድል የቤተሰቦቻችን ገዳዮች የተበቀልን ይመስለን ነበር። በፍጥነት የመግደልም ውድድር
ነበር፡፡እኔ አንዱን ምርኮኛ በፍጥነት ስለገደልኩ ተጨበጨበልኝ።ትልቅ ገድል እንደፈፀምኩ ተሰማኝ ። ለእኔ እና ኬን ታናሽ መቶ አለቃ እና ታናሽ ሐምሳ አለቃ የሚል ማዕረግ በቅደም ተከተል
ተሰጠን። ደስታችንን አደንዛዥ ዕፅ እና የጦርነት ፊልም በማየት ገለፅን፡፡
የግሌ ድንኳን ነበረኝ እንቅልፍ ስሌለኝ ተኝቼበት አላውቅም።አንዳንድ ቀን በውድቅት ለሊት ለስለስ ያለው ንፋስ ላንሳ የሚባል ጓደኛየን ዝማሬ ያስታውሰኛል። ዛፎቹ የእሱን ዝማሬ
ሚያንሾሻሽኩ ይመስላሉ:: ትንሽ ካዳመጥኩ በኋላ ደጋግሜ
እተኩስ እና ድምጹን አስወግዳለሁ ።
በምርኮ ይዘን ወደ ዋና ማዕከላችን የቀየርነው መንደር እና በጉዞችን የምናድርባቸው ጫካዎች ቤቴ ሆኑ፡፡ የጦር ጓዶቼ ቤተሰቤ ! መሳሪያዬ የፈለኩትን ማገኝበት እና ጠባቂየ ሲሆን
መግደል ወይም መገደል ደግሞ የምኖርበት ህግ ወይም ደንብ ሆነ። ሃሳቤ ከዚህ በላይ አይሻገርም። ከሁለት አመታት በላይ ተዋጋን መግደል የሌተ ቀን ተግባራችን ሆነ፡፡ ለማንም አላዝንም:: እንደልጅ ሳልኖር ልጅነቴን ሳላውቀው ሳላጣጥመውም ነጎደ። የቀን እና ለሊቱን መፈራረቅ ማውቀው በፀሐይ እና
ጨረቃ መውጣት ወይም መጥለቅ ብቻ ነው። እሁድ ይሁን አርብ ግን አላውቅም::
ህይወቴ ጤናማ ይመስለኝ ነበር። ጥር 1996 አስራ አምስት አመት ሲሞላኝ ግን ይሄ መቀየር ጀመረ
አንድ ቀን ሃያ የሚሆኑ የጦር ጓዶቼን ይዤ ጥይት ለማግኘት ባውያ ወደ ምትባል
#ክፍል_አስራ_ሁለት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
ቀኖቼን በወታደራዊ ስራዎች ተጠምጄ ባሳለፍኩ ቁጥር የራስ ምታቴ እየተሻለኝ መጣ፡፡ ቀን ቀን ኳስ መጫወት ትቼ ጥበቃ
ላይ እሰማራለሁ። ነጩን ክኒን በብዛት አዘውትሬ እወስድ ነበር።
ክኒኖቹ ሱስ ሁነውብኛል። ብዙ ኃይል ይሰጡኛል። መጀመሪያ አብዝቼ የወሰድኩ ቀን በጣም አልቦኝ ሁሉንም ልብሶቼን አውልቄ ነበር። ሰውነቴ ይንቀጠቀጣል፤ ዕይታየ ደበዘዘ ብዥታ
ለደቂቃዎች ያህል መስማትም አልቻልኩም። ያለ ምንም ስራ
መንደሩን እዞረዋለሁ፤ እረፍት የለኝም ብዙ ኃይል ይሰማኛል ነገር ግን ደንዝዣለሁ ስሜት አይሰማኝም፡፡ ክኒኑን አብዝቼ
መውሰዴን ቀጠልኩ።ምንም ነገር አይሰማኝም ብዙ ኃይል ከማግኘት እና ለሳምንት እንቅልፍ ካለመተኛት በስተቀር። ማታ ማታ ፊልም እናያለን። የጦርነት ፊልሞች፥ራምቦ፣ ፈርስት ብለድ፣ ራምቦ ሁለት፣ ኮማንዶ እና ሌሎች በጄነሬተር ወይም በመኪና ባትሪ በመታገዘ እንመለከት ነበር። ሁላችንም እንደ
ራምቦ መሆን እንፈልግ ነበር። እሱ ያደረጋቸውን እንቅስቃሴዎች ለመተግበር እንጓጓ ነበር።
ምግብ፣ መድሃኒት፣ ጥይቶች እና ጋዝ እያለቀብን ሲመጣ በከተማ፣ በገጠር መንደሮች እና በጫካ ውስጥ የሚገኙ
በር የአማጺዎችን ካምፖችን መውረር ጀመርን። ያልታጠቁ ሰዎች የሚገኝባቸውን ሌሎች መንደሮችን በማጥቃት ወታደሮችን መለመልን፡፡
“መልካም ዜና ደርሶናል ከመልዕክተኞቻችን የተወሰኑ አማጺዎችን ለመግደል እና በመጀመሪያም የእኛ የሆነውን ቁሳቁሳቸውን ለመውሰድ ከአምስት ደቂቃ በኋላ ከዚህ እንቀሳቀሳለን” አለ መቶ አለቃ አዋጁን ሲነግር። ፊቱ ላይ ልበ ሙሉነት ይነበባል። ግንባራችን ላይ አረንጓዴ ጨርቅ አስረን
ነበር ታዳጊዎች ይመሩ ነበር። ምንም አይነት ካርታ ምንም አይነት ጥያቄም አልተነሳም:: ቀጣይ ትዕዛዝ እስከሚሰጠን ድረስ እንዲሁ መንገድ እንድንከተል ነበር የተነጋገርነው ሰርዲን ለመብላት እና ነጩን ክኒን ለመውሰድ ከቆምንበት ውጭ ለብዙ ሰአታት
ያለማቋረጥ ተጓዝን፡፡ ክኒኖቹ ብዙ ኃይል
ከመስጠታቸውም በላይ ደፋር አደረጉን፡፡ የሞት ሃሳብ በጭራሽ ወደ አዕምሮዬ አልመጣም፡፡ መግደል ግን ውሃ እንደመጠጣት ቀላል ሆነ። የመጀመሪያውን ሰው ስገድል ብቻ ልቤ ተነክቶ ነበር። ከዛ በኋላ ግን ምንም አይነት ሃዘን ፀፀት አልተሰማኝም::
ከበላን በኋላ መድሃኒቱን ወስደን አዋቂዎች ለተወሰነ ደቂቃ እረፍት እስኪወስዱ ዙሪያውን ለጥበቃ እንሰማራለን። ከ አልሃጂ ጋር ነበርኩ፡፡ የጥይት መያዣውን በፍጥነት መቀየርን
እየተወዳደርን ነበር።
“ቆይ አንድ ቀን ልክ እንደ ራምቦ ብቻየን አንድ ሙሉ መንደር እቆጣጠራለሁ” አል ሃጂ ፈገግ እያለ እቅዱን ነገረኝ።
ልክ እንደ ኮማንዶ ፊልም የራሴ ባዙቃ እንዲኖረኝ እፈልጋለሁ። ያምራል።” አልኩ እና አንድ ላይ ሳቅን፡፡
ወደ አማጺዎች ካምፕ ከመግባታችን በፊት መንገዳችን ቀይረን በጫካው ውስጥ በመጓዝ አሰሳ አናደርጋለን፡፡ ካምፑ ዕይታችን ውስጥ ከገባ በኋላሸ ከበባ እናደርግ እና የመቶ አለቃን ትዕዛዝ
እንጠብቃለን። አማጺዎች ከአንዱ ወደ አንዱ ይንቀሳቀሳሉ ፣ሌሎቹ ግድግዳ ተገድፈው ሲቀመጡ እንደእኛ ያሉ ታዳጊዎች ደግሞ ይጠብቃሉ:: አማጺዎችን ባየኋቸው ቁጥር ደሜ
ይፈላል፤ እናደዳለሁ። አማጺዎቹ ቤተሰቤን ያጣሁበትን መንደር አውድመው ካርታ የተጫወቱት ይመስሉኛል። ስለዚህ መቶ አለቃ ትዕዛዝ ሲሰጥ የቻልኩትን ያህል እተኩሳለሁ። ንዴቴ አይወጣልኝም! ከተኩስ በኋላ ወደ ካምፑ እንገባለን፡፡ የቆሰሉትን
እንገድላለን ፤ ቤት ውስጥ ገብተን ጋዝ፣ አደንዛዥ እፆች፣ ጫማ፣የእጅ ስዓቶች፣ ሩዝ፣ ዓሳ፣ ጨው እና ሌሎች ነገሮችን
እንሰበስባለን።ያልታጠቁ ሰዎችን (ሲቪል) ሰብስበን የዘረፍነውንእንዲሸከሙ እናደርጋለን።
“እኛ” መቶ አለቃ ወደ እኛ እየጠቆመ ” ልንጠብቃችሁ ነው እዚህ ያለነው። ምንም አይነት ጉዳት እንዳይደርስባችሁ የምንችለውን እናደርጋለን።” አለ ወደ ያልታጠቁት ሰዎች እየጠቆመ።
“የእኛ ስራ ጥብቅ ነው፤ ሃገራቸውን ለመጠበቅ ምንም አይነት መስዋዕትነት ለመክፈል የተዘጋጁ ጎበዝ ወታደሮችም
አሉን። እኛ እንደ አማጺዎች አይደለንም። እነዛ ነፍስ ገዳዮች ያለ ምንም ምክንያት ሰው ይገድላሉ፤ ሁሉንም ሰው በጅምላ
ይጨፈጭፋሉ። እኛ ግን የሃገራችንን ለመጠበቅ፤ አገራችን ከእነሱ ክፋት እና ጥፋት ለማዳን ስንል ብቻ እንገድላቸዋለን።ስለዚህ ለእነዚህ የሃገራችሁ ጠባቂዎች ክብር ስጡ” ብሎ መቶ አለቃ ረጂም ንግግር አደረገ። ንግግሩ ሁለት ዓላማ ነበረው።
አንዱ በሲቪሎች ስለ እኛ ጥሩ አመለካከት እንዲኖራቸው ማድረግ ሲሆን ሌላው ደግሞ የእኛን ሞራል መገንባት ነበር።ጠበንጃየን ይዤ ቁሜለሁ። ልዩ የመሆን ስሜት ተሰማኝ፣የተፈላጊነት ፤ አንድ ትልቅ እና ጥብቅ ነገር ተሳታፊ መሆን እና ከአሁን በኋላ ደግሞ ከማንም አልሸሽም።ሽጉጤ አለኝ አስር አለቃ ሁልጊዜ እንደሚለው “ ይሄ መሳሪያ በዚህ ጊዜ የሃይላችሁ ምንጭ ነው:: ይጠብቃችኋል! እንዴት መጠቀም እንዳለባችሁ ካወቃችሁ ደግሞ የምትፈልጉትን ሁሉ ይሰጣችኋል።
መቶ አለቃ ንግግሩን ለማድረግ ምን እንደገፋፋው አላስታውስም። ብዙ ነገሮች ያለ ምንም ምክንያት ወይም ማብራሪይ ይሰሩ ነበር። አንዳንዴ ፊልም እያየን መሐል ላይ ድንገት ለጦርነት እንድንቀሳቀስ እንጠየቃለን። ከስዓታት በኋላ እንዳልተፈጠረ ከማስታወቂያ በኋላ እንደተመለስ ፊልሙን ካቆምንበት
እንቀጥላለን። ሁሌም ውጊያ ላይ ነን ወይ የጦርነት ፊልም እየተመለክትን ነው ወይ ደግሞ አደንዛዥ ዕፅ እየወሰድን ነው።
ብቻችን የምንሆንበት የምናስብበት ምንም አይነት ጊዜ የለም::እርስበርሳችን ስናወራ የምናወራው ስለተመለከትነው የጦርነት ፊልሞች እና መቶ አለቃ፣ አስር አለቃ ወይም ከእኛ አንዳችን ስለፈፅምነው ጀብድ ብቻ ነበር። ከዛ ውጭ ሌላ አለም ያለ አይመስለንም ነበር።
ከመቶ አለቃ ንግግር በኋላ ተራ በተራ ምርኮኞችን በአሰቃቂ ሁኔታ ገደልን። አማጺዎችን ስንገድል የቤተሰቦቻችን ገዳዮች የተበቀልን ይመስለን ነበር። በፍጥነት የመግደልም ውድድር
ነበር፡፡እኔ አንዱን ምርኮኛ በፍጥነት ስለገደልኩ ተጨበጨበልኝ።ትልቅ ገድል እንደፈፀምኩ ተሰማኝ ። ለእኔ እና ኬን ታናሽ መቶ አለቃ እና ታናሽ ሐምሳ አለቃ የሚል ማዕረግ በቅደም ተከተል
ተሰጠን። ደስታችንን አደንዛዥ ዕፅ እና የጦርነት ፊልም በማየት ገለፅን፡፡
የግሌ ድንኳን ነበረኝ እንቅልፍ ስሌለኝ ተኝቼበት አላውቅም።አንዳንድ ቀን በውድቅት ለሊት ለስለስ ያለው ንፋስ ላንሳ የሚባል ጓደኛየን ዝማሬ ያስታውሰኛል። ዛፎቹ የእሱን ዝማሬ
ሚያንሾሻሽኩ ይመስላሉ:: ትንሽ ካዳመጥኩ በኋላ ደጋግሜ
እተኩስ እና ድምጹን አስወግዳለሁ ።
በምርኮ ይዘን ወደ ዋና ማዕከላችን የቀየርነው መንደር እና በጉዞችን የምናድርባቸው ጫካዎች ቤቴ ሆኑ፡፡ የጦር ጓዶቼ ቤተሰቤ ! መሳሪያዬ የፈለኩትን ማገኝበት እና ጠባቂየ ሲሆን
መግደል ወይም መገደል ደግሞ የምኖርበት ህግ ወይም ደንብ ሆነ። ሃሳቤ ከዚህ በላይ አይሻገርም። ከሁለት አመታት በላይ ተዋጋን መግደል የሌተ ቀን ተግባራችን ሆነ፡፡ ለማንም አላዝንም:: እንደልጅ ሳልኖር ልጅነቴን ሳላውቀው ሳላጣጥመውም ነጎደ። የቀን እና ለሊቱን መፈራረቅ ማውቀው በፀሐይ እና
ጨረቃ መውጣት ወይም መጥለቅ ብቻ ነው። እሁድ ይሁን አርብ ግን አላውቅም::
ህይወቴ ጤናማ ይመስለኝ ነበር። ጥር 1996 አስራ አምስት አመት ሲሞላኝ ግን ይሄ መቀየር ጀመረ
አንድ ቀን ሃያ የሚሆኑ የጦር ጓዶቼን ይዤ ጥይት ለማግኘት ባውያ ወደ ምትባል
👍1
ትንሽ ከተማ ሄድኩ፡፡ በደቡብ በኩል የአንድ ቀን የእግር ጉዞ ነበረ። ጓደኞቼ አል ሃጂ እና ኬን ም ከእኔ ጋር ነበሩ።ከዛ የተመደበውን ጁማህን ለማየት ጓጉተን ነበር። የውጊያ ገጠመኞቹን እና ስንት ሰው እንደገደለ መስማት ፈልገናል። መቶ
አለቃንም ማግኘት ፈልጌ ነበር። ስለ ሼክስፔየር ለማውራት ጊዜ ይኖረናል የሚልም ተስፋ ነበረኝ፡፡
በአቧራማው መንገድ ዳር እና ዳር ሁለት ረድፍ ሰርተን ጥቅጥቅ ያለውን ጫካ ደም በለበሱ አይኖቻችንን እያየን መጓዝ
ጀመርን። ጀንበሯ ስትዘቀዝቅ ወደ ባውያ ከተማ ዳርቻ ተቃረብን። እኛ እዛው ስንቆይ አዛዣችን ወደፊት ሄደ። ከተወሰኑ
ደቂቃዎች በኋላ ወደ ከተማው እንድንገባ ምልክት ሰጠን፡፡
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
አለቃንም ማግኘት ፈልጌ ነበር። ስለ ሼክስፔየር ለማውራት ጊዜ ይኖረናል የሚልም ተስፋ ነበረኝ፡፡
በአቧራማው መንገድ ዳር እና ዳር ሁለት ረድፍ ሰርተን ጥቅጥቅ ያለውን ጫካ ደም በለበሱ አይኖቻችንን እያየን መጓዝ
ጀመርን። ጀንበሯ ስትዘቀዝቅ ወደ ባውያ ከተማ ዳርቻ ተቃረብን። እኛ እዛው ስንቆይ አዛዣችን ወደፊት ሄደ። ከተወሰኑ
ደቂቃዎች በኋላ ወደ ከተማው እንድንገባ ምልክት ሰጠን፡፡
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_አስራ_ሶስት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
መሳሪያየን አንግቼ ከኬን እና አል ሃጂ ወደ ከተማው ገባን።በከተማው ያሉ ግንብ ቤቶች ከእኛ ከተማ እና እስከ አሁን
ካየሁቸው መንደሮች ካሉ ቤቶች ትልቅ ናቸው፡፡ በዙሪያ ብዙ የማላውቃቸው አይቻቸው የማላውቅ ሰዎች አየሁ፡፡ ራሳችንን ዝቅ እያደረግን ሰላምታ ከተሰጣጣን በኋላ ጁማህን መፈለግ
ጀመርን። ፊቱን ወደ ጫካው ያዞረ ጡብ ቤት ደጃፍ ላይ ዥዋዥዌ ላይ ተቀምጦ ነበር። ከጎኑ መሳሪያ ነበር። ቀስ ብለን ወደ እሱ ስንጠጋ ፊቱን አዞሮ አየን።
ከባድ መሳሪያ ይዘህ ነው ምትዞረው ማለት ነው?” ብሎ አል ሃጂ ቀለደ።
“እንግዲህ ምን ታረገዋለህ! ከ AK ከፍ እያልኩ ነው” ብሎ መለሰ።ሁላችንም ሳቅን።
ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ እንደምንመለስ ነግረነው ጥይት እና ምግብ ልንጭን ወደ መጋዝን ሄድን።መጋዝን እያለን አዛዣችን፥ መቶ አለቃ “ዛሬን ከዚህ እደሩ፤ እራት ተዘጋጅቷል” እንዳለ ነገረን፡፡ አልራበኝም፡ ስለዚህ ኬን እና አል ሃጂ ወደ እራት
ሲሄድ እኔ ተለይቼ ወደ ጁማህ ተመልሼ ሄድኩ። ማውራት ከመጀመሩ በፊት ለደቂቃዎች ዝም ብለን ተቀመጥን፡፡
ነገ በጥዋት ለውጊያ ስለምወጣ ከመሄዳችሁ በፊት አላይህም” ብሎ ዝም አለ እና መሳሪያውን እየነካካ ቀጠለ:
የዚህን መሳሪያ ባለቤት ገደልኩት።
ብዙዎቻችንን ከገደለ በኋላ ነበር የደረስኩበት። ከዛ በኋላ ነበር እኔ የያዝኩት ”ብሎ ፈገግ አለ፡፡ እጃችንን አጋጨንና ሳቅን።ወዲያውኑ እንድንሰበሰብ ተጠራን:: ተሰባስቦ መጫወቻ እና
የአዛዦችን መተዋወቂያ ማህበራዊ ፕሮግራም ነበር። ጁማህ መሳሪያውን በአንድ እጁ ከያዘ በኋላ በሌላ እጁ ጫንቃየ ላይ አድርጎ አቅፎኝ ወደ መሰብሰቢያው ሜዳ ሄድን።ኬን እና አል
ሃጂ ከዛው እያጨሱ ነበሩ። መቶ አለቃም በቦታው ነበር። ትንሽ ፈንጠዝያ ነበር። የመቶ አለቃ ጓደኞች አብዛኞቹ ማለትም ሃምሳ አለቃ ማንሳራይ እና አስር አለቃ ጋዳፊ ሙተዋል። እሱ እንዴት
እንደተረፈ አይታወቅም። በተዕምር ምኑም ሳይነካ የለአንዳች ጠባሳ ተርፎ ሌሎች ሃይለኛ እና ታዛዥ ጓዶችን በሞቱ ጓደኞቹ ምትክ ለማፍራት በቅቷል።መቶ አለቃ ጋር ስለ ሼክስፔየር ማውራት ፈልጌ ነበር። ነገር ግን እሱ በማስተባበር ፤ ሰላም በመስጠት ተጠምዶ ነበር። በመጨረሻ እኔ ፊት ለ ፊት ሲደርስ
እጄን ጥብቅ አርጎ ያዘና “ማክቤዝ አይበገርም፧ ታላቁ የብሪያም ጫካ ዶንከን ኮረብታ እስኪደርስ ድረስ ማክቤዝ እጅ አይሰጥም አለ።
ጮክ ብሎ ”ልለያችሁ ነው ጓዶች” አለ። እጅ ከነሳን በኋላ እጁን እያውለለበ ሄደ። እኛም መሳሪያችን ከፍ አድርገን በጩኸት
ሰላምታችን ገለጸን። መቶ አለቃ ከሄደ በኋላ የሴራሊዮንን ብሄራዊ መዝሙር መዘመር ጀመርን። “ከፍ አድርገን
እናከብርሻለን፤ የነጻ ህዝቦች ሃገር፤ ጥልቅ ነው ለአንቺ ያለን ፍቅር” ለሊቱን ሙሉ ስንጫወት ስናወራ አሳለፍን።
ከመንጋቱ በፊት ጁማህ እና የተወሰኑ ወታደሮች ለውጊያ ሄዱ። አል ሃጂ፣ ኬን እና እኔ በሚቀጥለው ጥየቃ ብዙ
እንደምንጫወት ቃል ገብተን ተሰናበትነው:: ጁማህ ፈገግታ ካሳየን በኋላ መሳሪያውን ጠበቅ አድርጎ ከያዘ በኋላ ወደ ጫካው ገባ፡፡
ከትንሽ ስዓታት በኋላ አንድ ትልቅ መኪና ወደ መንደር መጣ፡፡ ዩኒሴፍ UNICEF የሚል ቲሸርት እና ጅንስ ሱሪ የለበሱ
አራት ሰዎች ከመኪናው ወርደው ወደ እኛ መጡ። አንድ ነጭ እና ቆዳዋ ነጣ ያለ ምንአልባት የሊባኖስ ሰው እና ሌሎቹ የሃገሩ ሰዎች ሴራሊዎናውያን ናቸው:: ጦርነቱን ያዩ አይመስሉም የተመቻቸው ነበሩ። ወደ መቶ አለቃ ተልከው የመጡ ይመስላሉ። እሱም ሲጠብቃቸው ነበር፡፡ ቤት ደጃፍ ተቀምጠው ሲያወሩ ከማንጎ ዛፍ ስር ተቀምጠን መሳሪያችንን
እየወለወልን እናያቸው ነበር። በኋላ መቶ አለቃ ከሁለቱ የውጭ ሃገር ሰዎች ጋር እጅ ተጨባበጠ፡፡ ጠባቂው ወደ እኛ መጣ እና እንድንሰለፍ ነገረን። ሰፈሩን እየዞረ ከ “ መቶ አለቃ የመጣ ትዕዛዝ ነው!” ትዕዛዝ መቀበል እና የታዘዝ ነውን መፈፀም ለምደናል። ወደ ጎን መስመር ሰርተን መጠበቅ ጀመርን።
መቶ አለቃ ከፊታችን ቁሞ ወታደራዊ ሰላምታ ሰጠን፡፡ ሌላ ግዳጅ እየጠበቅን ነበር፡፡ “አሳርፍ” ብሎ ቀስ ብሎ መራመድ
መቃኘት ጀመረ፡፡ እንግዶቹ ከጀርባ ነበሩ።
“ስጠቁም ወደ ጠባቂየ በመሄድ ትሰለፋላችሁ ገብቷችሃል።”ሲል “አዎ! አለቃ” ብለን ጮህን፡፡
“አንተ፣ አንተ.....” መቶ አለቃ እየመረጠ እስከ ሰልፉ መጨረሻ ደረሰ፡፡ መቶ አለቃ እኔን ሲመርጠኝ አትኩሬ ተመለከትኩት።
እሱ ግን አላየኝም:: አል ሃጂም ተመረጠ። ኬን ግን ትልቅ ስለሆነ አልተመረጠም:: “መሳሪያችሁን የጥይት ካዝና አወላልቃችሁ መሬት ላይ አስቀምጡ” የሚል ትዕዛዝ ከመቶ አለቃ ሰጠ፡፡ መሳሪያችንን አወላልቀን መሬት ላይ አስቀመጥን።መቶ አለቃን ተከትለን እንግዶች ወደ የመጡበት ገልባጭ መኪና ሄድን። መቶ አለቃ ፊቱን ወደ እኛ ሲያዞር ቆምን “ ጎበዝ ጀግና
ወታደር ነበራችሁ! ታውቃላችሁ የዚህ ወንድማማችነት እና ሃገርን የማዳን ጥሪ አካል እንደነበራችሁ። ከእናንተ ጋር ሃገሬን
በማገልገሌ ክብር ይሰማኛል። ኮርቼባችዋለሁ። አሁን ስራችሁ
እዚህ ጋ ያበቃል። ልለቃችሁ ይገባል። እነዚህ ሰዎች ትምህርት ቤት ያስገቧችኋል፤ ሌላ መልካም ህይወት እንዲኖሩዋችሁ ይረድዋችኋል።” ይሄን ብቻ ነበር ተናግሮ ትቶን ሄደ:: ቀጥሎ
ፍተሻ ነበር። ሰንጢ እና ቦምብ ይዤ ስለነበር መፈተሽ አልፈለኩም፡ ፈታሹን ብትነካኝ እገልሃለሁ ብየ ዛትኩበት። ከእኔ
ጎን ወደ አለው ቀጠለ።
ምን እየሆነ እንዳለ አልገባኝም? መቶ አለቃ ለእነዚህ ሰዎች ለምን አሳልፎ ሊሰጠን እንደወሰነ አልገባኝም። ጦርነቱ እስኪበቃ ድረስ የምንቀጥል መስሎን ነበር፡፡ ግን ያለምንም ማብራሪያ
ተወሰድን፡፡
መኪና ውስጥ የደንብ ልብሳቸው ንጹህ እና መሳሪያቸው አዲስ የሆነ ሶስት ፖሊሶች ነበሩ። ፖሊሶቹ ከገልባጩ ወርደው እኛ እንድንወጣ ጠቆሙን። ወጥተን ሁለት አግድም ወንበሮች
ላይ ፊት ለ ፊት ተቀመጥን። ፖሊሶች መውረጃው ላይ ተቀመጥን።
አል ሃጂ እና እኔ በመገረም በብስጭት ተያየን። የት እንደሚወስዱን እንኳ አናውቅም። ለስዓታት ተጓዝን። ያለምንም ስራ ቁጭ ብሎ መጓዙ አድካሚም
አሰልቺም ነበር፡፡ መኪናውን ጠልፎ ወደ ባውያ ለመመለስ አሰብኩ። መሳሪያውን ለመንጠቅ ስዘጋጅ መኪናው ለፍተሻ
ፍጥነቱን ቀንሶ ፖሊሶቹ ወረዱ።
መቀመጥ ስላልቻልኩ በጉዞ በሙሉ እረፍት አልነበረኝም ያቁነጠንጠኝ ነበር። የፍተሻ ጣቢያዎች ስንደርስ ትንሽ ፈታ እል ነበር። በመጨረሻ ፍተሻ ጣቢያ ያገኘናቸው ወታደሮች የሚያምር ደንብ ልብስ የለበሱ መሳርያቸው አዲስ ነበር።
በኮሮኮንች መንገድ የመጨረሻ ፍተሻ ጣቢያውን አልፈን እንደሄድን የተጨናነቀ የአስፓልት መንገድ ደረስን። ዙሪያውን
መኪኖች በተለያየ አቅጣጫ ሲጓዙ አየሁ፡፡ በህይወቴ የዚህን ያህል ብዙ መኪኖች አይቼ አላውቅም፡፡ መርሰዲሶች፣ቶዮታዎች፣ማዝዳዎች፣ቼርቮያለ ትዕግስት ሲያጮሁ ሙዚቃ ሲያጫውቱ ነበር፡፡ የት እንደምንሄድ አሁንም አላውቅም ነገር ግን Freetown ፍሪታውን የሴራሊዮን ዋና ከተማ እንዳለን
አውቂያለሁ።ለምን እንደሆነ ግን አላወቅኩም፡፡
ውጩ እየጨለመ ነው። መኪናችን በዝግታ ወደ ተጨናነቀው መንገድ ሲገባ የመንገድ መብራቶች ተራ በተራ
እንደፍንጣቂ ነገር ቦግ ቦግ እያሉ መብራት ጀመሩ። የሱቆች እና
የመጠጥ ቤት መብራቶች ሳይቆጠር ብዙ መንገድ መብራቶች ከተማዋን አንቆጥቁጠዋታል። የከተማዋ ፎቆቹም በብዙ ብርሃን የተንቆጠቆጡ ናቸው። ለተወሰኑ ደቂቃዎች በፍጥነት
#ክፍል_አስራ_ሶስት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
መሳሪያየን አንግቼ ከኬን እና አል ሃጂ ወደ ከተማው ገባን።በከተማው ያሉ ግንብ ቤቶች ከእኛ ከተማ እና እስከ አሁን
ካየሁቸው መንደሮች ካሉ ቤቶች ትልቅ ናቸው፡፡ በዙሪያ ብዙ የማላውቃቸው አይቻቸው የማላውቅ ሰዎች አየሁ፡፡ ራሳችንን ዝቅ እያደረግን ሰላምታ ከተሰጣጣን በኋላ ጁማህን መፈለግ
ጀመርን። ፊቱን ወደ ጫካው ያዞረ ጡብ ቤት ደጃፍ ላይ ዥዋዥዌ ላይ ተቀምጦ ነበር። ከጎኑ መሳሪያ ነበር። ቀስ ብለን ወደ እሱ ስንጠጋ ፊቱን አዞሮ አየን።
ከባድ መሳሪያ ይዘህ ነው ምትዞረው ማለት ነው?” ብሎ አል ሃጂ ቀለደ።
“እንግዲህ ምን ታረገዋለህ! ከ AK ከፍ እያልኩ ነው” ብሎ መለሰ።ሁላችንም ሳቅን።
ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ እንደምንመለስ ነግረነው ጥይት እና ምግብ ልንጭን ወደ መጋዝን ሄድን።መጋዝን እያለን አዛዣችን፥ መቶ አለቃ “ዛሬን ከዚህ እደሩ፤ እራት ተዘጋጅቷል” እንዳለ ነገረን፡፡ አልራበኝም፡ ስለዚህ ኬን እና አል ሃጂ ወደ እራት
ሲሄድ እኔ ተለይቼ ወደ ጁማህ ተመልሼ ሄድኩ። ማውራት ከመጀመሩ በፊት ለደቂቃዎች ዝም ብለን ተቀመጥን፡፡
ነገ በጥዋት ለውጊያ ስለምወጣ ከመሄዳችሁ በፊት አላይህም” ብሎ ዝም አለ እና መሳሪያውን እየነካካ ቀጠለ:
የዚህን መሳሪያ ባለቤት ገደልኩት።
ብዙዎቻችንን ከገደለ በኋላ ነበር የደረስኩበት። ከዛ በኋላ ነበር እኔ የያዝኩት ”ብሎ ፈገግ አለ፡፡ እጃችንን አጋጨንና ሳቅን።ወዲያውኑ እንድንሰበሰብ ተጠራን:: ተሰባስቦ መጫወቻ እና
የአዛዦችን መተዋወቂያ ማህበራዊ ፕሮግራም ነበር። ጁማህ መሳሪያውን በአንድ እጁ ከያዘ በኋላ በሌላ እጁ ጫንቃየ ላይ አድርጎ አቅፎኝ ወደ መሰብሰቢያው ሜዳ ሄድን።ኬን እና አል
ሃጂ ከዛው እያጨሱ ነበሩ። መቶ አለቃም በቦታው ነበር። ትንሽ ፈንጠዝያ ነበር። የመቶ አለቃ ጓደኞች አብዛኞቹ ማለትም ሃምሳ አለቃ ማንሳራይ እና አስር አለቃ ጋዳፊ ሙተዋል። እሱ እንዴት
እንደተረፈ አይታወቅም። በተዕምር ምኑም ሳይነካ የለአንዳች ጠባሳ ተርፎ ሌሎች ሃይለኛ እና ታዛዥ ጓዶችን በሞቱ ጓደኞቹ ምትክ ለማፍራት በቅቷል።መቶ አለቃ ጋር ስለ ሼክስፔየር ማውራት ፈልጌ ነበር። ነገር ግን እሱ በማስተባበር ፤ ሰላም በመስጠት ተጠምዶ ነበር። በመጨረሻ እኔ ፊት ለ ፊት ሲደርስ
እጄን ጥብቅ አርጎ ያዘና “ማክቤዝ አይበገርም፧ ታላቁ የብሪያም ጫካ ዶንከን ኮረብታ እስኪደርስ ድረስ ማክቤዝ እጅ አይሰጥም አለ።
ጮክ ብሎ ”ልለያችሁ ነው ጓዶች” አለ። እጅ ከነሳን በኋላ እጁን እያውለለበ ሄደ። እኛም መሳሪያችን ከፍ አድርገን በጩኸት
ሰላምታችን ገለጸን። መቶ አለቃ ከሄደ በኋላ የሴራሊዮንን ብሄራዊ መዝሙር መዘመር ጀመርን። “ከፍ አድርገን
እናከብርሻለን፤ የነጻ ህዝቦች ሃገር፤ ጥልቅ ነው ለአንቺ ያለን ፍቅር” ለሊቱን ሙሉ ስንጫወት ስናወራ አሳለፍን።
ከመንጋቱ በፊት ጁማህ እና የተወሰኑ ወታደሮች ለውጊያ ሄዱ። አል ሃጂ፣ ኬን እና እኔ በሚቀጥለው ጥየቃ ብዙ
እንደምንጫወት ቃል ገብተን ተሰናበትነው:: ጁማህ ፈገግታ ካሳየን በኋላ መሳሪያውን ጠበቅ አድርጎ ከያዘ በኋላ ወደ ጫካው ገባ፡፡
ከትንሽ ስዓታት በኋላ አንድ ትልቅ መኪና ወደ መንደር መጣ፡፡ ዩኒሴፍ UNICEF የሚል ቲሸርት እና ጅንስ ሱሪ የለበሱ
አራት ሰዎች ከመኪናው ወርደው ወደ እኛ መጡ። አንድ ነጭ እና ቆዳዋ ነጣ ያለ ምንአልባት የሊባኖስ ሰው እና ሌሎቹ የሃገሩ ሰዎች ሴራሊዎናውያን ናቸው:: ጦርነቱን ያዩ አይመስሉም የተመቻቸው ነበሩ። ወደ መቶ አለቃ ተልከው የመጡ ይመስላሉ። እሱም ሲጠብቃቸው ነበር፡፡ ቤት ደጃፍ ተቀምጠው ሲያወሩ ከማንጎ ዛፍ ስር ተቀምጠን መሳሪያችንን
እየወለወልን እናያቸው ነበር። በኋላ መቶ አለቃ ከሁለቱ የውጭ ሃገር ሰዎች ጋር እጅ ተጨባበጠ፡፡ ጠባቂው ወደ እኛ መጣ እና እንድንሰለፍ ነገረን። ሰፈሩን እየዞረ ከ “ መቶ አለቃ የመጣ ትዕዛዝ ነው!” ትዕዛዝ መቀበል እና የታዘዝ ነውን መፈፀም ለምደናል። ወደ ጎን መስመር ሰርተን መጠበቅ ጀመርን።
መቶ አለቃ ከፊታችን ቁሞ ወታደራዊ ሰላምታ ሰጠን፡፡ ሌላ ግዳጅ እየጠበቅን ነበር፡፡ “አሳርፍ” ብሎ ቀስ ብሎ መራመድ
መቃኘት ጀመረ፡፡ እንግዶቹ ከጀርባ ነበሩ።
“ስጠቁም ወደ ጠባቂየ በመሄድ ትሰለፋላችሁ ገብቷችሃል።”ሲል “አዎ! አለቃ” ብለን ጮህን፡፡
“አንተ፣ አንተ.....” መቶ አለቃ እየመረጠ እስከ ሰልፉ መጨረሻ ደረሰ፡፡ መቶ አለቃ እኔን ሲመርጠኝ አትኩሬ ተመለከትኩት።
እሱ ግን አላየኝም:: አል ሃጂም ተመረጠ። ኬን ግን ትልቅ ስለሆነ አልተመረጠም:: “መሳሪያችሁን የጥይት ካዝና አወላልቃችሁ መሬት ላይ አስቀምጡ” የሚል ትዕዛዝ ከመቶ አለቃ ሰጠ፡፡ መሳሪያችንን አወላልቀን መሬት ላይ አስቀመጥን።መቶ አለቃን ተከትለን እንግዶች ወደ የመጡበት ገልባጭ መኪና ሄድን። መቶ አለቃ ፊቱን ወደ እኛ ሲያዞር ቆምን “ ጎበዝ ጀግና
ወታደር ነበራችሁ! ታውቃላችሁ የዚህ ወንድማማችነት እና ሃገርን የማዳን ጥሪ አካል እንደነበራችሁ። ከእናንተ ጋር ሃገሬን
በማገልገሌ ክብር ይሰማኛል። ኮርቼባችዋለሁ። አሁን ስራችሁ
እዚህ ጋ ያበቃል። ልለቃችሁ ይገባል። እነዚህ ሰዎች ትምህርት ቤት ያስገቧችኋል፤ ሌላ መልካም ህይወት እንዲኖሩዋችሁ ይረድዋችኋል።” ይሄን ብቻ ነበር ተናግሮ ትቶን ሄደ:: ቀጥሎ
ፍተሻ ነበር። ሰንጢ እና ቦምብ ይዤ ስለነበር መፈተሽ አልፈለኩም፡ ፈታሹን ብትነካኝ እገልሃለሁ ብየ ዛትኩበት። ከእኔ
ጎን ወደ አለው ቀጠለ።
ምን እየሆነ እንዳለ አልገባኝም? መቶ አለቃ ለእነዚህ ሰዎች ለምን አሳልፎ ሊሰጠን እንደወሰነ አልገባኝም። ጦርነቱ እስኪበቃ ድረስ የምንቀጥል መስሎን ነበር፡፡ ግን ያለምንም ማብራሪያ
ተወሰድን፡፡
መኪና ውስጥ የደንብ ልብሳቸው ንጹህ እና መሳሪያቸው አዲስ የሆነ ሶስት ፖሊሶች ነበሩ። ፖሊሶቹ ከገልባጩ ወርደው እኛ እንድንወጣ ጠቆሙን። ወጥተን ሁለት አግድም ወንበሮች
ላይ ፊት ለ ፊት ተቀመጥን። ፖሊሶች መውረጃው ላይ ተቀመጥን።
አል ሃጂ እና እኔ በመገረም በብስጭት ተያየን። የት እንደሚወስዱን እንኳ አናውቅም። ለስዓታት ተጓዝን። ያለምንም ስራ ቁጭ ብሎ መጓዙ አድካሚም
አሰልቺም ነበር፡፡ መኪናውን ጠልፎ ወደ ባውያ ለመመለስ አሰብኩ። መሳሪያውን ለመንጠቅ ስዘጋጅ መኪናው ለፍተሻ
ፍጥነቱን ቀንሶ ፖሊሶቹ ወረዱ።
መቀመጥ ስላልቻልኩ በጉዞ በሙሉ እረፍት አልነበረኝም ያቁነጠንጠኝ ነበር። የፍተሻ ጣቢያዎች ስንደርስ ትንሽ ፈታ እል ነበር። በመጨረሻ ፍተሻ ጣቢያ ያገኘናቸው ወታደሮች የሚያምር ደንብ ልብስ የለበሱ መሳርያቸው አዲስ ነበር።
በኮሮኮንች መንገድ የመጨረሻ ፍተሻ ጣቢያውን አልፈን እንደሄድን የተጨናነቀ የአስፓልት መንገድ ደረስን። ዙሪያውን
መኪኖች በተለያየ አቅጣጫ ሲጓዙ አየሁ፡፡ በህይወቴ የዚህን ያህል ብዙ መኪኖች አይቼ አላውቅም፡፡ መርሰዲሶች፣ቶዮታዎች፣ማዝዳዎች፣ቼርቮያለ ትዕግስት ሲያጮሁ ሙዚቃ ሲያጫውቱ ነበር፡፡ የት እንደምንሄድ አሁንም አላውቅም ነገር ግን Freetown ፍሪታውን የሴራሊዮን ዋና ከተማ እንዳለን
አውቂያለሁ።ለምን እንደሆነ ግን አላወቅኩም፡፡
ውጩ እየጨለመ ነው። መኪናችን በዝግታ ወደ ተጨናነቀው መንገድ ሲገባ የመንገድ መብራቶች ተራ በተራ
እንደፍንጣቂ ነገር ቦግ ቦግ እያሉ መብራት ጀመሩ። የሱቆች እና
የመጠጥ ቤት መብራቶች ሳይቆጠር ብዙ መንገድ መብራቶች ከተማዋን አንቆጥቁጠዋታል። የከተማዋ ፎቆቹም በብዙ ብርሃን የተንቆጠቆጡ ናቸው። ለተወሰኑ ደቂቃዎች በፍጥነት
👍1
ከተጓዝን በኋላ መኪናዋ ቆመች፡፡ ከመኪና ወርደን አራት የ ዩኒሴፍ UNICEF ሰራተኞችን ተከትለን አንድ ትልቅ ግቢ ውስጥ ገባን።
ግቢው ብዙ ቤቶች አሉት:: በእኛ እድሜ የሚገኙ ታዳጊ ወንዶችን ደጃፍ ላይ ራሳቸውን አጉብጠው ተቀምጠዋል። ሊያዩን አልፈለጉም፧ ለምን ከዚህ እንደመጡ አላወቁም፥ ግራ ተጋብተዋል፡፡ ሊባኖሳዊ የሚመሰለው ሰውየ ወደ አንዱ ቤት በመውሰድ ከዛ እንደምንቆይ እና የምንተኛበትን አልጋ አሳየን።
በየኣንዳንዳችን ቁም ሳጥን ውስጥ ሳሙና፣ የጥርስ ሳሙና፣ የጥርስ ቡርሽ፣ ፎጣ እና ንጹህ ቲ ሸርት እንደተቀመጠ በደስታ ነገረን፡፡ ነገ ደግሞ ጫማ ትውስዳላችሁ አለ። ምንም አይነት
ስሜት አላሳየንም፡፡
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ግቢው ብዙ ቤቶች አሉት:: በእኛ እድሜ የሚገኙ ታዳጊ ወንዶችን ደጃፍ ላይ ራሳቸውን አጉብጠው ተቀምጠዋል። ሊያዩን አልፈለጉም፧ ለምን ከዚህ እንደመጡ አላወቁም፥ ግራ ተጋብተዋል፡፡ ሊባኖሳዊ የሚመሰለው ሰውየ ወደ አንዱ ቤት በመውሰድ ከዛ እንደምንቆይ እና የምንተኛበትን አልጋ አሳየን።
በየኣንዳንዳችን ቁም ሳጥን ውስጥ ሳሙና፣ የጥርስ ሳሙና፣ የጥርስ ቡርሽ፣ ፎጣ እና ንጹህ ቲ ሸርት እንደተቀመጠ በደስታ ነገረን፡፡ ነገ ደግሞ ጫማ ትውስዳላችሁ አለ። ምንም አይነት
ስሜት አላሳየንም፡፡
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#እስኪምን_አለበት !?
ፈገግታሽ . . .
እንደ በጋ መብረቅ
አንዴ ብልጭ ብሎ ፣ ዓመት የሚቀድስ
ዘመን የሚያስቀድስ ፤
ሣቅሽ . . .
ደራሽ አውሎ ነፋስ ፤
ሐዘን ግብስብሱን ባ'ንደዜ የሚያድስ።
እንባሽ . . .
የጤዛ ጠብታ ፣
ካ'ስፈሪው ዝናብ ላይ እፍታን ጨልፎ
እምቡጥ ጉንጮችሽ ላይ በጨረፍታ አርፎ
( ዕፎይታ የሚሰጥ ፤ ገጸ ውበት ኾነ ! )
ዝምታሽ . . .
ልክ እንደ ደመና ፤
የፀሓዩን ንዳድ ፣ የጨረቃን ጮራ
ሰማይና አድማሱን . . .
በግርዶሽ ያስረዋል አንዳች ሳያወራ።
ታዲያ ምን አለበት . . .?!
አንድ ጊዜ ብቻ ፣
አንድ'ዜ ብቅ ብለሽ
ከጎጄዬ መጥተሽ
ከ'ልፍኜ ተገኝተሽ
ቤቴን ብታደምቂው ፤
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
ፈገግታሽ . . .
እንደ በጋ መብረቅ
አንዴ ብልጭ ብሎ ፣ ዓመት የሚቀድስ
ዘመን የሚያስቀድስ ፤
ሣቅሽ . . .
ደራሽ አውሎ ነፋስ ፤
ሐዘን ግብስብሱን ባ'ንደዜ የሚያድስ።
እንባሽ . . .
የጤዛ ጠብታ ፣
ካ'ስፈሪው ዝናብ ላይ እፍታን ጨልፎ
እምቡጥ ጉንጮችሽ ላይ በጨረፍታ አርፎ
( ዕፎይታ የሚሰጥ ፤ ገጸ ውበት ኾነ ! )
ዝምታሽ . . .
ልክ እንደ ደመና ፤
የፀሓዩን ንዳድ ፣ የጨረቃን ጮራ
ሰማይና አድማሱን . . .
በግርዶሽ ያስረዋል አንዳች ሳያወራ።
ታዲያ ምን አለበት . . .?!
አንድ ጊዜ ብቻ ፣
አንድ'ዜ ብቅ ብለሽ
ከጎጄዬ መጥተሽ
ከ'ልፍኜ ተገኝተሽ
ቤቴን ብታደምቂው ፤
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_አስራ_አራት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
“ኑ ወደ ማዕድ ቤት ትንሽ ምግብ ያስፈልጋችኋል።” አለ ሴራሊዮናዊው የዩኒሴፍ ሰራተኛ፡፡ ተከተልነው።
በማዕድ ቤቱ ውስጥ አግድም ወንበርአ ላይ ከሌሎች ልጆች ጋር ተቀመጥን። ሩዝ በጎድጓዳ ስሃን ቀረበልን፡፡ እሱን ያለምንም
ፋታ መብላት ጀመርን። አል ሃጂ ከየት ናችሁ ብሎ እስከሚጠይቅ ድረስ ምንም አላወራንም: አል ሃጂ ሲጠይቃቸው
ደስተኛ አልነበሩም:: ማነህ አንተ? ያንተን ጥያቄ ልንመልስ ነው የመጣነው?” ሲል አል ሃጂ ተነስቶ ገፈተረው። ልጁ ተነስቶ
ሊደባደብ ሲል አንድ ሰው ተዉ ልጆች!” አለ።
ቦምብ አውጥቼ ይሄ የመጨረሻችሁ እንዲሆን ነው የምትፈልጉት ወይስ ጥያቄውን ትመልሳላችሁ?” አልኩ፡፡
ከኬኖ ወረዳ ነው የመጣነው”
“አልማዝ ከሚገኝበት አካባቢ?” አለ አል ሃጂ።
“ከጦሩ ጋር ነው ወይስ ለአማጺዎች ነው የተዋጋችሁት?”
ምኔ አማጺ ይመስላል? ለጦሩ ወግኜ ነው የተዋጋሁት።
አማጺዎች መንደሬን አቃጥለው ወላጆቼን ገለዋል፤ አንተ ግን እነሱን ትመስላለህ።”
በአንድ ወገን ነዋ የተዋጋነው” አለ አል ሃጂ። ተቀመጥን።ቦምቡን እንደያዝኩት ነበር። ፊቴን ወደ ማዕድ ቤቱ ያመጣን
ሰውየ አዙሬ “ መቶ አለቃ ለምን ለእነዚህ ያልታጠቁ ሴታ ሴት ሰዎች አሳልፈው እንደሰጡን ታውቃለህ?” ብየ ጠየቅኩት።
በፍርሃት ርዶ፣ በላብ ተጠምቆ ሊመልስ ሲል አንዱ ልጅ “ እሱ ያልታጠቀ ነው ሌሎች ልጆችን እንጠይቃቸው”አለ። ማቡ ይባል ነበር በኋላ ጓደኛሞች ሁነናል፡፡ ተነስተን ቤት ደጃፍ ላይ ወደ ተቀመጡት ታዳጊዎች ሄድን፡፡
“ጓዶች አዛጋችሁ ለምን ለእነዚህ ሰዎች እንደሰጡዋችሁ ታውቃላችሁ?” ብሎ አል ሃጂ ጠየቀ። ዝም አሉ፡፡ “ኣትሰሙም
እንዴ?
“ማንም እንዲያስቸግረን አንፈልግም” አለ በሸካራ ድምጸ።በዛ ላይ ላልታጠቀ ተራ ሰው ጥያቄ መልስ መስጠት አንፈል
ግም።”
“ተራ ሰው ሲቪል አይደለንም! አለ ማቡ በቁጣ።” ተራ ያልታጠቀ ሰው ካለ እናንተ ናችሁ። መለዮ እንኳን ያልለበሳ
ችሁ። ምን አይነት ወታደር ነው መለዮ ማይለብሰው ባካችሁ?!”
“ለአማጺዎች ነው የተዋጋ ነው፤ ጦሩ ጠላታችን ነው።ለነጻነት ነው የተዋጋነው! ጦሩ ቤተሰቤን ገድሏል መንደሬንም
አፍርሷል፡፡የጦሩን አባላት ባገኘሁት አጋጣሚ ሁሉ እገላለሁ”ብሎ ተነሳ።
“አማጺዎች” ብሎ ማቡ ጮኸ። ሰንጢዎቻችን አውጥተን ተፋጠጥን፡፡ እንደገና ጦርነት! ፈረንጆቹ ቦታ ስለቀየርን ከጦር ቀጠና ስለተገለልን ብቻ ደህና የምንሆን መስሏቸዋል።አዕምሮችን የተበረዘ አደገኛ ነፍሰ ገዳይ መሆናችንን አላወቁም! አሁን በቀላሉ እንደማናገግም ይገባቸዋል።
ቦምብ ወረወርኩ ግን ዘገየ፡፡ ድብድቡ ቀጠለ አንዳንዶቻችን ሰንጢ ይዘን ሌሎች በባዶ እጅ መታገል ጀመርን። አንዱን እግሩን ወጋሁት ሌላው እኔን ሊወጋ ሲል አል ሃጂ ቀድሞ ከጀርባ ወጋው፡፡ የጮኸ ወይም ያለቀስ የለም ሁላችንም ለምደነዋል በዛ ላይ አደገኛ ዕፅ ወስደን ነበር፡፡ ፖሊሶቹ “አቁሙ አቁሙ” እያሉ
ወደ እኛ መጡ፡፡ከአገላገሉን በኋላ የወደቀውን ሊያነሱ ሲጎነበሱ ገፍትረን ጥለን መሳሪያቸውን ቀማን። ማቡ ተኩሶ የተወሰኑትን ገደለ ሌሎችን ደግሞ አቆሰለ፡፡ አማጺዎች ከእኛ ወገን ሁለት
ታዳጊዎችን ገደሉ፡፡ ፖሊስ ወደ ሰማይ ቢተኩስም መታገል አላቆምንም:: ስለዚህ በጉልበት ለያዩን መሳሪያ ድቅነው
አቆሙን። አምቡላንስ እየጮኸ መጥቶ የተጎዱትን ወሰደ።ስድስት ታዳጊዎች ሲሞቱ ሁለት ፖሊሶችን ጨምሮ ብዙዎች
ቆሰሉ።
በማቡ ጀብድ ተገረምን፤ማዕድ ቤት ተመልሰን ስለእሱ ነበር የምናወራው። አንዱን ልጅ አይኑን መትቶት ልጁ ቡጢ ሊመልስ ቢፈልግም ማቡን ማየት አልቻለም። ድብድብ ረብሻው ለእኛ
ጨዋታ ነበር። ከማዕድ ቤት አውጥተው ወሰዱን። የጦር መኪና እየጠበቀን ነበር፡፡ “ወደ ጦርነቱ ሊመልሱን መሆን አለበት::” አለ አል ሃጂ። ዝም ብለን ብሔራዊ መዝሙሩን መዘመር ጀመርን::ወደ ጦርነቱ አልመለሱንም ነገር ግን ቤኒን ቤት ወደ ሚባል ሌላ የማገገሚያ ማዕከል ነበር የወስዱን፡፡ ለምን ወደ እዚህ ቦታ
እንደመጣን አሁንም አላወቅኩም፡፡ G3 ሽጉጤ፣ የጦርነት ፊልም እና የምወስደው ክኒን ትዝ ይለኛል። ከሁሉም በላይ መቶ
አለቃ “ከአሁን በኋላ ያገኘነውን አማጺ እንገላለን፧ ምህረት ምርኮኛ የሚባል ነገር የለም”የሚለው ንግግር ወደ አዕምሮየ
ይመላለስ ነበር።
ባልታጠቀ በሲቪል መታዘዝ ያበሳጫል፡፡ ድምጻቸውን መስማት እንኳ አልፈልግም:: ለቁርስ እንኳ ሲጠሩን ሳጥን ያገኘሁትን ነገር በቡጢ እመታለሁ። ከመመገብ ውጭ የታዘዝነውን አንፈፅምም ነበር።
እንቢተኛ ነበርን! ቁርስ ሻይ እና ዳቦ፣ ምሳ እና እራት ደግሞ ሩዝ እና ሾርባ እንበላ ነበር። መሳሪያችን እና አደገኛ ዕፅ ከእኛ
ጋር ስላልነበር ደስተኞች አልነበርንም።
ተደጋጋሚ የጤና ምርመራ እና የምክር አገልግሎት በነርሶቹ እና ሌሎች ሰራተኞች ይደረግልን ነበር፡፡ አንወደውም ነበር፡፡ ገና
ሲጀምሩ ያገኘነውን እቃ እንወረውራለን እንደበድባቸዋለን።ከምግብ በኋላ ያለምንም ምክንያት እንደባደብ ነበር። ሰራተኞቹ ምንም ብናደርግ እነሱን እንኳ ብንደበድባቸው አያዝኑብንም።
“የእናንተ ጥፋት አይደለም እንደዚህ ልታደርጉ የቻላችሁት”ብለው ፈገግታ ያሳዩናል።በእኛ ተስፋ ላለመቁረጥ የተስማሙ ይመስላሉ።
የራስ ምታት ማይግሬን እንደገና ተንስቶ ያሰቃየኝ ጀምሯል። አንጥረኛ በመዶሻ ራሴን የሚቀጠቅጥ ይመስለኛል።
አንዳንድ ቀን ራሴን መቆጣጠር ከብዶኝ መሬት ላይ እንከባለላሁ:: አል ሃጂ ደግሞ የቤቱን ምሰሶ በመደብደብ ሆስፒታል ገብቶ ነበር፡፡ ቆይቼ እኔም ራሴን ስቼ ሆስፒታል ገባሁ:: ሰውነቴን ሙሉ ያመኝ ነበር፤ ጉሮሮየ ደርቆ የማጥወልወል ስሜት ይሰማኝ ነበር። ነርሷ ፈገግታ እያሳየች ወደ እኔ አልጋ መጥታ መርፌ ወጋችኝ። አካሌ ተዳክሞ ተኛሁ።
በሚቀጥለው ቀን ከሆስፒታል ወጣሁ። ነርሷ ውሃ በደንብ ጠጣ አለች::
አንዳንዴ ከማጥወልወል ስሜት እና ድንገት እራስን ስቶ ከመውደቅ ባለፈ ከሁለት ወር በኋላ በአብዛኛው እየተሻለን
መጣ፡ የጦርነቱ መጥፎ ትዝታዎች ትርፍ ጊዜ ስለነበረን ወደ አዕምሮዋችን እየመጣ ያስጨንቀን ነበር። ይሄን ለማስረሳት ይመስላል ትምህርት ትጀምራላችሁ ተብለን የትምህርት
መሳሪያዎች ተሰጠን። ደብተር፣ እስክርቢቶ እና እርሳስ ከተሰጠን በኋላ ከሰኞ እስከ አርብ ከአራት ስዓት እስከ አስራ ሁለት ስዓት ትምህርቱ እንደሚሰጥ ተነገረን።ወዲያው ግን የተሰጠንን የትምህርት መሳሪያዎች አቃጠልን።
እንደገና ተሰጠን። እንደገና አቃጠልነው፡፡
አንድ ቀን ቀትር ላይ የማገገሚያው ሰራተኛች የተወሰነ የትምህርት መሳሪያዎች ደጃፍ አስቀምጠው ሂዱ። ማቡ የትምህርት መሳሪያዎችን አየና ለምን አንሸጠውም የሚል ሃሳብ
አመጣ። “ማን ይገዛናል? ሰዎች ይፈሩናል? አለ አንድ ታዳጊ ልጅ፡፡ “የሚረከበን ነጋዴ እንፈልጋለን” አለ ማቡ። በፕላስቲክ ቦርሳ ተሸክመን ቅርብ ወደ ሚገኝ ገቢያ ወስደን ለአከፋፋይ
ሸጥነው:: “ብዙ ገንዘብ ነው ያገኘነው” አለ ማቡ። ምሳ እንዳያመልጠን ወደ ማዕከሉ ቶሎ ተመልሰን። ከምሳ በኋላ ማቡ ድርሻችንን አከፋፈለ። ግማሾቹ ኮካ ኮላ፣ ከረሜላ እና ሌሎች ነገሮች ሲገዙ ማቡ፣ አል ሃጂ እና እኔ ደግሞ ለሽርሽር ወደ ፍሪ ታውን ለመሄድ አቀድን።
ጥዋት ቶሎ ቶሎ በላይ በላይ ቁርሳችንን ከበላን በኋላ አንድ በ አንድ ሾልከን ከመመገቢያ አዳራሹ ወጣን። ከውጭ ከተገናኘን በኋላ አውቶብስ መጠበቅ ጀመርን።
“ከተማውን ታውቁታላችሁ? ከዚህ በፊት ወደ ከተማው
ሂዳችሁ ታውቃላችሁ?”
#ክፍል_አስራ_አራት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
“ኑ ወደ ማዕድ ቤት ትንሽ ምግብ ያስፈልጋችኋል።” አለ ሴራሊዮናዊው የዩኒሴፍ ሰራተኛ፡፡ ተከተልነው።
በማዕድ ቤቱ ውስጥ አግድም ወንበርአ ላይ ከሌሎች ልጆች ጋር ተቀመጥን። ሩዝ በጎድጓዳ ስሃን ቀረበልን፡፡ እሱን ያለምንም
ፋታ መብላት ጀመርን። አል ሃጂ ከየት ናችሁ ብሎ እስከሚጠይቅ ድረስ ምንም አላወራንም: አል ሃጂ ሲጠይቃቸው
ደስተኛ አልነበሩም:: ማነህ አንተ? ያንተን ጥያቄ ልንመልስ ነው የመጣነው?” ሲል አል ሃጂ ተነስቶ ገፈተረው። ልጁ ተነስቶ
ሊደባደብ ሲል አንድ ሰው ተዉ ልጆች!” አለ።
ቦምብ አውጥቼ ይሄ የመጨረሻችሁ እንዲሆን ነው የምትፈልጉት ወይስ ጥያቄውን ትመልሳላችሁ?” አልኩ፡፡
ከኬኖ ወረዳ ነው የመጣነው”
“አልማዝ ከሚገኝበት አካባቢ?” አለ አል ሃጂ።
“ከጦሩ ጋር ነው ወይስ ለአማጺዎች ነው የተዋጋችሁት?”
ምኔ አማጺ ይመስላል? ለጦሩ ወግኜ ነው የተዋጋሁት።
አማጺዎች መንደሬን አቃጥለው ወላጆቼን ገለዋል፤ አንተ ግን እነሱን ትመስላለህ።”
በአንድ ወገን ነዋ የተዋጋነው” አለ አል ሃጂ። ተቀመጥን።ቦምቡን እንደያዝኩት ነበር። ፊቴን ወደ ማዕድ ቤቱ ያመጣን
ሰውየ አዙሬ “ መቶ አለቃ ለምን ለእነዚህ ያልታጠቁ ሴታ ሴት ሰዎች አሳልፈው እንደሰጡን ታውቃለህ?” ብየ ጠየቅኩት።
በፍርሃት ርዶ፣ በላብ ተጠምቆ ሊመልስ ሲል አንዱ ልጅ “ እሱ ያልታጠቀ ነው ሌሎች ልጆችን እንጠይቃቸው”አለ። ማቡ ይባል ነበር በኋላ ጓደኛሞች ሁነናል፡፡ ተነስተን ቤት ደጃፍ ላይ ወደ ተቀመጡት ታዳጊዎች ሄድን፡፡
“ጓዶች አዛጋችሁ ለምን ለእነዚህ ሰዎች እንደሰጡዋችሁ ታውቃላችሁ?” ብሎ አል ሃጂ ጠየቀ። ዝም አሉ፡፡ “ኣትሰሙም
እንዴ?
“ማንም እንዲያስቸግረን አንፈልግም” አለ በሸካራ ድምጸ።በዛ ላይ ላልታጠቀ ተራ ሰው ጥያቄ መልስ መስጠት አንፈል
ግም።”
“ተራ ሰው ሲቪል አይደለንም! አለ ማቡ በቁጣ።” ተራ ያልታጠቀ ሰው ካለ እናንተ ናችሁ። መለዮ እንኳን ያልለበሳ
ችሁ። ምን አይነት ወታደር ነው መለዮ ማይለብሰው ባካችሁ?!”
“ለአማጺዎች ነው የተዋጋ ነው፤ ጦሩ ጠላታችን ነው።ለነጻነት ነው የተዋጋነው! ጦሩ ቤተሰቤን ገድሏል መንደሬንም
አፍርሷል፡፡የጦሩን አባላት ባገኘሁት አጋጣሚ ሁሉ እገላለሁ”ብሎ ተነሳ።
“አማጺዎች” ብሎ ማቡ ጮኸ። ሰንጢዎቻችን አውጥተን ተፋጠጥን፡፡ እንደገና ጦርነት! ፈረንጆቹ ቦታ ስለቀየርን ከጦር ቀጠና ስለተገለልን ብቻ ደህና የምንሆን መስሏቸዋል።አዕምሮችን የተበረዘ አደገኛ ነፍሰ ገዳይ መሆናችንን አላወቁም! አሁን በቀላሉ እንደማናገግም ይገባቸዋል።
ቦምብ ወረወርኩ ግን ዘገየ፡፡ ድብድቡ ቀጠለ አንዳንዶቻችን ሰንጢ ይዘን ሌሎች በባዶ እጅ መታገል ጀመርን። አንዱን እግሩን ወጋሁት ሌላው እኔን ሊወጋ ሲል አል ሃጂ ቀድሞ ከጀርባ ወጋው፡፡ የጮኸ ወይም ያለቀስ የለም ሁላችንም ለምደነዋል በዛ ላይ አደገኛ ዕፅ ወስደን ነበር፡፡ ፖሊሶቹ “አቁሙ አቁሙ” እያሉ
ወደ እኛ መጡ፡፡ከአገላገሉን በኋላ የወደቀውን ሊያነሱ ሲጎነበሱ ገፍትረን ጥለን መሳሪያቸውን ቀማን። ማቡ ተኩሶ የተወሰኑትን ገደለ ሌሎችን ደግሞ አቆሰለ፡፡ አማጺዎች ከእኛ ወገን ሁለት
ታዳጊዎችን ገደሉ፡፡ ፖሊስ ወደ ሰማይ ቢተኩስም መታገል አላቆምንም:: ስለዚህ በጉልበት ለያዩን መሳሪያ ድቅነው
አቆሙን። አምቡላንስ እየጮኸ መጥቶ የተጎዱትን ወሰደ።ስድስት ታዳጊዎች ሲሞቱ ሁለት ፖሊሶችን ጨምሮ ብዙዎች
ቆሰሉ።
በማቡ ጀብድ ተገረምን፤ማዕድ ቤት ተመልሰን ስለእሱ ነበር የምናወራው። አንዱን ልጅ አይኑን መትቶት ልጁ ቡጢ ሊመልስ ቢፈልግም ማቡን ማየት አልቻለም። ድብድብ ረብሻው ለእኛ
ጨዋታ ነበር። ከማዕድ ቤት አውጥተው ወሰዱን። የጦር መኪና እየጠበቀን ነበር፡፡ “ወደ ጦርነቱ ሊመልሱን መሆን አለበት::” አለ አል ሃጂ። ዝም ብለን ብሔራዊ መዝሙሩን መዘመር ጀመርን::ወደ ጦርነቱ አልመለሱንም ነገር ግን ቤኒን ቤት ወደ ሚባል ሌላ የማገገሚያ ማዕከል ነበር የወስዱን፡፡ ለምን ወደ እዚህ ቦታ
እንደመጣን አሁንም አላወቅኩም፡፡ G3 ሽጉጤ፣ የጦርነት ፊልም እና የምወስደው ክኒን ትዝ ይለኛል። ከሁሉም በላይ መቶ
አለቃ “ከአሁን በኋላ ያገኘነውን አማጺ እንገላለን፧ ምህረት ምርኮኛ የሚባል ነገር የለም”የሚለው ንግግር ወደ አዕምሮየ
ይመላለስ ነበር።
ባልታጠቀ በሲቪል መታዘዝ ያበሳጫል፡፡ ድምጻቸውን መስማት እንኳ አልፈልግም:: ለቁርስ እንኳ ሲጠሩን ሳጥን ያገኘሁትን ነገር በቡጢ እመታለሁ። ከመመገብ ውጭ የታዘዝነውን አንፈፅምም ነበር።
እንቢተኛ ነበርን! ቁርስ ሻይ እና ዳቦ፣ ምሳ እና እራት ደግሞ ሩዝ እና ሾርባ እንበላ ነበር። መሳሪያችን እና አደገኛ ዕፅ ከእኛ
ጋር ስላልነበር ደስተኞች አልነበርንም።
ተደጋጋሚ የጤና ምርመራ እና የምክር አገልግሎት በነርሶቹ እና ሌሎች ሰራተኞች ይደረግልን ነበር፡፡ አንወደውም ነበር፡፡ ገና
ሲጀምሩ ያገኘነውን እቃ እንወረውራለን እንደበድባቸዋለን።ከምግብ በኋላ ያለምንም ምክንያት እንደባደብ ነበር። ሰራተኞቹ ምንም ብናደርግ እነሱን እንኳ ብንደበድባቸው አያዝኑብንም።
“የእናንተ ጥፋት አይደለም እንደዚህ ልታደርጉ የቻላችሁት”ብለው ፈገግታ ያሳዩናል።በእኛ ተስፋ ላለመቁረጥ የተስማሙ ይመስላሉ።
የራስ ምታት ማይግሬን እንደገና ተንስቶ ያሰቃየኝ ጀምሯል። አንጥረኛ በመዶሻ ራሴን የሚቀጠቅጥ ይመስለኛል።
አንዳንድ ቀን ራሴን መቆጣጠር ከብዶኝ መሬት ላይ እንከባለላሁ:: አል ሃጂ ደግሞ የቤቱን ምሰሶ በመደብደብ ሆስፒታል ገብቶ ነበር፡፡ ቆይቼ እኔም ራሴን ስቼ ሆስፒታል ገባሁ:: ሰውነቴን ሙሉ ያመኝ ነበር፤ ጉሮሮየ ደርቆ የማጥወልወል ስሜት ይሰማኝ ነበር። ነርሷ ፈገግታ እያሳየች ወደ እኔ አልጋ መጥታ መርፌ ወጋችኝ። አካሌ ተዳክሞ ተኛሁ።
በሚቀጥለው ቀን ከሆስፒታል ወጣሁ። ነርሷ ውሃ በደንብ ጠጣ አለች::
አንዳንዴ ከማጥወልወል ስሜት እና ድንገት እራስን ስቶ ከመውደቅ ባለፈ ከሁለት ወር በኋላ በአብዛኛው እየተሻለን
መጣ፡ የጦርነቱ መጥፎ ትዝታዎች ትርፍ ጊዜ ስለነበረን ወደ አዕምሮዋችን እየመጣ ያስጨንቀን ነበር። ይሄን ለማስረሳት ይመስላል ትምህርት ትጀምራላችሁ ተብለን የትምህርት
መሳሪያዎች ተሰጠን። ደብተር፣ እስክርቢቶ እና እርሳስ ከተሰጠን በኋላ ከሰኞ እስከ አርብ ከአራት ስዓት እስከ አስራ ሁለት ስዓት ትምህርቱ እንደሚሰጥ ተነገረን።ወዲያው ግን የተሰጠንን የትምህርት መሳሪያዎች አቃጠልን።
እንደገና ተሰጠን። እንደገና አቃጠልነው፡፡
አንድ ቀን ቀትር ላይ የማገገሚያው ሰራተኛች የተወሰነ የትምህርት መሳሪያዎች ደጃፍ አስቀምጠው ሂዱ። ማቡ የትምህርት መሳሪያዎችን አየና ለምን አንሸጠውም የሚል ሃሳብ
አመጣ። “ማን ይገዛናል? ሰዎች ይፈሩናል? አለ አንድ ታዳጊ ልጅ፡፡ “የሚረከበን ነጋዴ እንፈልጋለን” አለ ማቡ። በፕላስቲክ ቦርሳ ተሸክመን ቅርብ ወደ ሚገኝ ገቢያ ወስደን ለአከፋፋይ
ሸጥነው:: “ብዙ ገንዘብ ነው ያገኘነው” አለ ማቡ። ምሳ እንዳያመልጠን ወደ ማዕከሉ ቶሎ ተመልሰን። ከምሳ በኋላ ማቡ ድርሻችንን አከፋፈለ። ግማሾቹ ኮካ ኮላ፣ ከረሜላ እና ሌሎች ነገሮች ሲገዙ ማቡ፣ አል ሃጂ እና እኔ ደግሞ ለሽርሽር ወደ ፍሪ ታውን ለመሄድ አቀድን።
ጥዋት ቶሎ ቶሎ በላይ በላይ ቁርሳችንን ከበላን በኋላ አንድ በ አንድ ሾልከን ከመመገቢያ አዳራሹ ወጣን። ከውጭ ከተገናኘን በኋላ አውቶብስ መጠበቅ ጀመርን።
“ከተማውን ታውቁታላችሁ? ከዚህ በፊት ወደ ከተማው
ሂዳችሁ ታውቃላችሁ?”
አልሃጂ ጠየቀን።
አይ ሂጄ አላውቅም” አልኩ::
' ለትምህርት ወደ ፍሪ ታውን ልመጣ ነበር ግን ጦርነቱ ቀድሞ ተከሰተ። ውብ ከተማ እንደሆነ ግን ሰምቻለሁ” አለ አል
ሃጂ።
“እንግዲህ ታውቁታላችሃ! አውቶብሱ መጥቷል” አለ ማቡ። እስከ አንቃሩ የተከፈተው ሙዚቃ ከሰው ጫጫታ ጋር
ተዳምሮ አውቶብሱ ገበያ መስሏል። የሚዳንሱ ሰዎችም ነበሩ።ከጀርባ ተቀምጠን የሚያልፉትን ቤቶች አና ሱቆች አየን።
መሃል ከተማው አካባቢ ኪሲ መንገድ ወረድን። ሰዎች ለዕለት ተዕለት ኑሮቸው ከዚያ ወደዚህ ይጣደፋሉ፡፡ ትላልቅ
ሱቆች በሁለቱም የመንገድ አቅጣጫ ሲገኙ የመንገድ አዟሪዎች መንገዱን አጣበው ይሸጣሉ። የአይን አዋጅ ሆነብን በቀላሉ ተማረክን”::
“ጥሩ እንደሚሆን ነግሬችሁ ነበር” አለ ማቡ በደስታ እየዘለለ።ይሄን ረዥም ፎቅ ተመልከት” ወደ አንድ በእጄ እያመለከትኩ።
“ ያን ተመልከት በጣም ረዥም ነው” ብሎ አል ሃጂ ጮኸ።
“ሰዎች እንዴት ነዉ እዛ ላይ የሚወጡት?” ብሎ ማቡ ጠየቀ።
ቀስ ብለን ሁሉን እየቃኘን ፤የመኪናውን ብዛት እና ሁሉም አይነት ምግቦች ባላቸው የሊባኖስ ሱቆች እየተደነቅን መራመድ ጀመርን፡፡ ስንዞር ከቆየን በኋላ የሃገሪቱ ብሔራዊ ምልክት ወደ
ሆነው የጥጥ ዛፍ ደረስን። አፋችንን ከፍተን አትኩረን ተመለከትነው:: ከዚህ በፊት ከገንዘብ ጀርባ ላይ ነበር ያየነው።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
አይ ሂጄ አላውቅም” አልኩ::
' ለትምህርት ወደ ፍሪ ታውን ልመጣ ነበር ግን ጦርነቱ ቀድሞ ተከሰተ። ውብ ከተማ እንደሆነ ግን ሰምቻለሁ” አለ አል
ሃጂ።
“እንግዲህ ታውቁታላችሃ! አውቶብሱ መጥቷል” አለ ማቡ። እስከ አንቃሩ የተከፈተው ሙዚቃ ከሰው ጫጫታ ጋር
ተዳምሮ አውቶብሱ ገበያ መስሏል። የሚዳንሱ ሰዎችም ነበሩ።ከጀርባ ተቀምጠን የሚያልፉትን ቤቶች አና ሱቆች አየን።
መሃል ከተማው አካባቢ ኪሲ መንገድ ወረድን። ሰዎች ለዕለት ተዕለት ኑሮቸው ከዚያ ወደዚህ ይጣደፋሉ፡፡ ትላልቅ
ሱቆች በሁለቱም የመንገድ አቅጣጫ ሲገኙ የመንገድ አዟሪዎች መንገዱን አጣበው ይሸጣሉ። የአይን አዋጅ ሆነብን በቀላሉ ተማረክን”::
“ጥሩ እንደሚሆን ነግሬችሁ ነበር” አለ ማቡ በደስታ እየዘለለ።ይሄን ረዥም ፎቅ ተመልከት” ወደ አንድ በእጄ እያመለከትኩ።
“ ያን ተመልከት በጣም ረዥም ነው” ብሎ አል ሃጂ ጮኸ።
“ሰዎች እንዴት ነዉ እዛ ላይ የሚወጡት?” ብሎ ማቡ ጠየቀ።
ቀስ ብለን ሁሉን እየቃኘን ፤የመኪናውን ብዛት እና ሁሉም አይነት ምግቦች ባላቸው የሊባኖስ ሱቆች እየተደነቅን መራመድ ጀመርን፡፡ ስንዞር ከቆየን በኋላ የሃገሪቱ ብሔራዊ ምልክት ወደ
ሆነው የጥጥ ዛፍ ደረስን። አፋችንን ከፍተን አትኩረን ተመለከትነው:: ከዚህ በፊት ከገንዘብ ጀርባ ላይ ነበር ያየነው።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#መንገድ
የመኼድ ርዝመት በዕርምጃ ስኬት
የሕይወትም ዳና በመሥመሩ ልኬት
ከተነጻጸረ . . .!
ይመተራል ዕድሜ ፣ ይሰበዛል ታሪክ
ይፍታታል ትርጓሜ ፣ በተጓዙበት ልክ።
ዕርምጃ - ፩
ዕንቅፋት በበዛው በጠባብ ጎዳና
ዐይነ ስውር ተጓዥ በእዝነ ልቦና ፣
ያለ መሪ ጒዞ በሐሳብ በትሩ
ያለመደናቀፍ ፣ መድረስ ከመንበሩ።
ዕርምጃ – ፪
በፍሥሓ ጕዝጓዝ ፣ በተደላደለ
የሚደነቃቀፍ ፣ ማየት ያልታደለ
ትላንቱን የረሳ ፣ በነግ አልባ ጕዘት
በለኮሰው እሳት ፣ ያልወጣ ከፍዘት።
እንግዲኽ . . .
በመንገድ ርቀት በ'ርምጃችን ዕድሜ
ከምንም መጀመር . . .
ያልጀመሩት ጉዞ የለም ፍጻሜ።
ለቅጽበት አይተሺኝ
በድኔን ዳብሰሺኝ
ያንቀላፋው ልቤን
ነክተሽ ብታነቂው።
እስኪ አኹን ምን ነበር . . . ?!
በምኞት ሠቀቀን ያ'ላንቺ ከምኖር
አንድ'ዜ ዳብሰሽኝ ዘላ'ለም ብቀበር።
እስኪ ምን አለበት . . . ?!
ፍቅርሽን ሰጥተሺኝ ፣
ሞትን ብንቅበት
ትንሣኤን ባውቅበት።
እስኪ ምን አለበት . . . ?!
ዘመኑን በሙሉ ባክኖ እንደኖረ
የመናፈቅ ዕድሜው በፍቅር ተሻረ።
( . . . የሚል ገድል ታሪክ . . . )
(. . . ተጽፎ ቢተረክ . . .)
እስኪ ምን አለበት . . .?!
ድንገት ተከስተሽ ፣
ፍካት ባጣው ቤቴ ፣ ሣቅሽን ብትዘሪበት
ብለሽ ብትነግሪያቸው ሕያውነት ቅጽበት።
የመኼድ ርዝመት በዕርምጃ ስኬት
የሕይወትም ዳና በመሥመሩ ልኬት
ከተነጻጸረ . . .!
ይመተራል ዕድሜ ፣ ይሰበዛል ታሪክ
ይፍታታል ትርጓሜ ፣ በተጓዙበት ልክ።
ዕርምጃ - ፩
ዕንቅፋት በበዛው በጠባብ ጎዳና
ዐይነ ስውር ተጓዥ በእዝነ ልቦና ፣
ያለ መሪ ጒዞ በሐሳብ በትሩ
ያለመደናቀፍ ፣ መድረስ ከመንበሩ።
ዕርምጃ – ፪
በፍሥሓ ጕዝጓዝ ፣ በተደላደለ
የሚደነቃቀፍ ፣ ማየት ያልታደለ
ትላንቱን የረሳ ፣ በነግ አልባ ጕዘት
በለኮሰው እሳት ፣ ያልወጣ ከፍዘት።
እንግዲኽ . . .
በመንገድ ርቀት በ'ርምጃችን ዕድሜ
ከምንም መጀመር . . .
ያልጀመሩት ጉዞ የለም ፍጻሜ።
ለቅጽበት አይተሺኝ
በድኔን ዳብሰሺኝ
ያንቀላፋው ልቤን
ነክተሽ ብታነቂው።
እስኪ አኹን ምን ነበር . . . ?!
በምኞት ሠቀቀን ያ'ላንቺ ከምኖር
አንድ'ዜ ዳብሰሽኝ ዘላ'ለም ብቀበር።
እስኪ ምን አለበት . . . ?!
ፍቅርሽን ሰጥተሺኝ ፣
ሞትን ብንቅበት
ትንሣኤን ባውቅበት።
እስኪ ምን አለበት . . . ?!
ዘመኑን በሙሉ ባክኖ እንደኖረ
የመናፈቅ ዕድሜው በፍቅር ተሻረ።
( . . . የሚል ገድል ታሪክ . . . )
(. . . ተጽፎ ቢተረክ . . .)
እስኪ ምን አለበት . . .?!
ድንገት ተከስተሽ ፣
ፍካት ባጣው ቤቴ ፣ ሣቅሽን ብትዘሪበት
ብለሽ ብትነግሪያቸው ሕያውነት ቅጽበት።
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_አስራ_አምስት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
...ቅጠሎቹ አረንጓዴ ሲሆኑ ግንዱ ግን በጣም አርጅቷል። “ይሄን ስንነግራቸው ማንም አያምነንም” አለ አል ሃጂ።
የእራት ስዓት እየደረሰ ስለነበር ወደ ማዕከል መመለስ ነበረብን፡፡ ያን ምሽት ጓደኞቻችን ስለ ረጃጂም ህንጻዎች :
መኪናዎች እና ገበያው ነገርናቸው፡፡ ሁሉም ደስ ብሏቸው ማየት ፈለጉ። ማዕከሉም ይሄን በመረዳት በሳምንት አንድ ቀን የሽርሽር ፕሮግራም ተያዘልን፡፡
ቀስ በቀስ ወደ ትምህርት ተመለስን። ቀለል ያለ የትምህርት ስርዓት ነበር፡፡ ለሂሳብ መደመር፣ማባዛት እና ማካፈል ስንማር እንግሊዝኛ ደግሞ ምንባብ ማንበብ፣ ቃላቶችን ትርጉም ማወቅ
እና የእጅ ጽሁፍ እንማራለን። ብዙም አንከታተልም ; ትኩረታችን በትንሽ ነገር ይሰረቃል። በእርሳስ እንወጋጋላን
እንደባደባለን። “የናንተ ጥፋት አይደለም
ወደፊት ትስተካከላላችሁ' ይለናል መምህሩ።
ከምሳ በኋላ የጠረጴዛ ቴንስ ወይም እግር ኳስ እንጫወት ነበር። ለሊት ግን አስጨናቂ ነበር። በቅዥት እንባንናለን፣ በላብ እንጠመቃለን፣ ጩኸት እና ግድግዳ መደብደብ ነበር። ሰራተኞቹ
ይህን ስለሚያውቁ ጥበቃ ያደርጉልን ነበር።
የሴራሊዮን ዝናባማ ወቅት ከግንቦት እስከ ጥቅምት ሲሆን ሐምሌ፣ ነሐሴ እና መስከረም ደግሞ ከባድ ዝናብ ይኖራል።
ዝናቡ አንዳንዴ የጦርነቱን መጥፎ ትዝታዎች ይቀሰቅስብኛል።
የሰለጠንኩበት ቦታ እና የሞሪባ ሞት ትዝ ይለኛል። ሞሪባ በተኩስ እሩምታ ሲገደል መቅበር ቀርቶ ማልቀስ እንኳ አልቻልንም። አንድ ዛፍ ላይ አስጠግተነው በአፉ ደም እየደፈቀ ትተነው ሄድን።
ሲነጋ ሰራተኛዋ ብርድ ልብሱን መልሳ እያለበሰችኝ “ያንተ ጥፋት አይደለም በፍጹም! አይዞህ ትረሳዋለህ ይሻልሃል”
ትለኛለች፡፡
አንድ ቀን ረፋድ ላይ ቴንስ ስንጫወት የግቢው ሰራተኞች በሙሉ ይመለከቱን ነበር። አንድ ሰው ከኋላ ትከሻዬ ላይ ሲነካኝ ተሰማኝ ። ነርሷ ነበረች ። ነጭ ደምብ ልብስ እና ነጭ ኮፍያ ለብሳለች። ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር ፊት ለ ፊት ሳያት። ነጭ ጥርሷ ከጥቁር እና አንጸባራቂ ቆዳዋ ጋር ተጣምሮ ልዩ ውበት
ሰጥቷታል። ስትስቅ ደግሞ የበለጠ ውበቷ ይፈካል። ረዥም ናት፤ ትልልቅ አይኖች አሏት፡፡ ጠርሙስ ኮካ ኮላ ሰጥታኝ በሚያስፈልግህ ጊዜ ና እና እየኝ” ብላ ፈገግታ ሰጥታኝ ሄደች::
ከአል ሃጂ ጋር ጨዋታውን ትተን ወደ ውጭ ወጣን እና ኮካውን መጠጣት ጀመርን። “ወዳሃለች” እያለ አል ሃጂ ሊቀልድብኝ ሞከረ። ምንም አላልኩም::
እህ ትወዳታለህ እንዴ?” ብሎ ጠየቀኝ፡፡
“ እኔ አላውቅም:: ትልቅ ናት በዛ ላይ ነርሳችን ናት” አልኩ።
ማለት ሴቶችን ትፈራለህ?” አለ
“አንተ እንደምታስበው ወዳኝ አይመስለኝም” ብየ አል ሃጂን
ተመለከትኩት። የምለውን ነገር እያዳመጠ ይስቃል።
ኮካውን ጠጥተን እንደጨረስን አል ሃጂ ሄደ እኔ ግን ወደ ሆስፒታል ለመሄድ ወሰንኩ፡፡ በሩ ስደርስ ነርሷ ስልክ እያወራች አየኋት። እንድገባ እና እንድቀመጥ በእጇ ምልክት አሳየችኝ።
ወዲያው ስልኳን አቁማ ፈገግታ እያሳየችኝ ወንበሯን ወደ እኔ
አቀረበች፡፡ ስለ ጦርነቱ ጥያቄ ልትጠይቀኝ እንደሆነ ገመትኩ።
እሷ ግን በተረጋጋ መንፈስ “ ስምህ ማነው” ብላ ጠየቀችኝ፡፡ገረመኝ! ስሜን እንደምታውቀው እርግጠኛ ነበርኩ። “ስሜን ታውቂዋለሽ” ብየ በቁጣ መለስኩ።
“ ምን አልባት ላውቀው እችላለሁ ግን ስምህን እንድትነግረኝ እፈልጋለሁ?” አለች አይኗን እያፈጠጠች::
እሺ እሺ እስማይል” አልኩ፡፡
“ጥሩ ስም” አለች እራሷን እየነቀነቀች፡፡ “ የእኔ ስም አስቴር ነው። ጓደኛሞች እንሁን።”
“እርግጠኛ ነሽ ከእኔ ጋር ጓደኛ መሆን ትፈልጊያለሽ” አልኳት::ለተወሰነ ጊዜ ካሰበች በኋላ “እርግጠኛ ላልሆን እችላለሁ” አለች።
ምን ማለት እንዳለብኝ ስላላወቅኩ እና ማንንም ስለማመን ለተወሰነ ጊዜ ዝም አልኩ። እንዴት መትረፍ እና እራሴን
መንከባከብ እንዳለብኝ ብቻ ነው ነበር የተማርኩት። እንደ መቶ አለቃ ጃባቲ ያሉ ያመንኳቸው የታዘዝኳቸው ሰዎች እንኳ
ሰዎችን በተለይ አዋቂዎችን እንድጠራጠር አድርገውኛል::
የሰዎችን ሃሳብ መጠራጠር ከጀመርኩ ቆይቻለሁ። ሰዎች ጓደኛ የሚሆኑት አንዱ ሌላው ላይ ጥቅም ለማግኘት ነው ብየ አስብ ነበር፡፡ ስለዚህ ለነርሷ ምንም መልስ አልሰጠኋትም።
“ያንተ ነርስ ነኝ በቃ ይሄ ነው። ከእኔ ጋር ጓደኛ መሆን ከፈለክ ልትጠይቀኝ እና ላምንህ ይገባል” አለች። ተመሳሳይ ሃሳብ
ስለነበረን ፈገግ አልኩ። ፈገግታህ ያምራል” አለች። አፍሬ ቁጥብ ሆንኩ።
“ከከተማ እንዳመጣልህ የምትፈልገው ነገር አለ?” ብላ ጠየቀችኝ፡፡ መልስ አልሰጠሁም::
“ለዛሬ ይበቃናል” አለች፡፡
ከተወሰነ ቀን በኋላ ነርሷ ስጦታ ሰጠችኝ። የተጠቀለለ ነገር ነበር ምን ይሆን እያልኩ መክፈት ጀመርኩ። ልክ እንዳየሁት በደስታ ተነስቼ አቀፍኳት። “ጓደኛ ካልሆን ለምን ይሄን ማዳመጫ እና ካሴት አመጣሽልኝ? ራፕ ሙዚቃ እንደምወድ እንዴት አወቅሽ?”
“እባክህ ተቀመጥ” አለች። የጆሮ ማዳመጫውን አደረኩ
D.M.C የዲ.ኤም.ሲ ሙዚቃ ነበር የምሰማው “It's like that and that the Way it is...” እንደዛ ነው እንደነገሩ” ራሴን ማንቀሳቀስ ጀመርኩ።አስቴር የጆሮ ማዳመጫውን ከጆሮዬ አውጥታ “አንተ ሙዚቃ ስታዳምጥ እኔ ልመረምርህ ነው”
አለች። ተስማማሁ። ምላሴን ፣ አይኔን አየች ከዛ እግሬን ስታይ ጠባሳ ነበረኝ። “ይሄ ጠባሳ እንዴት ወጣብህ?”
“በጥይት ተመትቼ ቆስየ ነው” እላለሁ በቀላሉ።
ፊቷ በሃዘን ተሞላ “ምን እንደሆንክ ምን እንደሚሰማህ ከነገርከኝ መድሃኒት ላዝልህ እችላለሁ” አለች። ሁሉንም
ነገርኳት፡፡ እንዴት በጥይት እንደተመታሁ፣
ስንት ጊዜ እንደተመታሁ እና ከዛ ምን እንዳደረኩ ነገርኳት። ልነግራት ግን
ፈልጌ አልነበረም፡፡ አስቃቂውን የጦርነቱን ክስተት ስነግራት መጠየቅ ታቆማለች ብዬ እንጂ። እሷ ግን በጥንቃቄ ታዳምጣለች። የትናንቱን ታሪኬን ማስታወስ ስጀምር አንገቴን ደፋሁ።
በበጋ ወቅት ስለነበረው ጦርነት ነገርኳት። ምግብ እና ጥይት ያጠረን አስቸጋሪ ወቅት ነበር። ሌላ መንደር ማጥቃት ነበረብን።ከትንሽ ስለላ በኋላ የሶስት ቀን ጉዞ ወደ ሚጠይቅ አንድ ሰፈር ሄድን። እቅዳችን ምግብ እና ጥይት ይዞ መምጣት ሳይሆን የምናጠቃውን ሰፈር ወደ ዋና ማዕከል መቀየር ነበር። ያለን
መሳሪያ እና ምግብ ይዘን ወጣን። ቦታው ደርሰን ለደፈጣ ውጊያ ስንዘጋጅ መንደሩ ባዶ መሆኑን ተገነዘብን። ከስዓት በኋላ
አምስት ታጣቂዎች መጥተው ባልዲ ይዘው ወደ ወንዙ ወረዱ..ገና መጠርጠር ስንጀምር ከኋላ ተኩስ ተከፈተብን። ለሊቱን ሙሉ ተታኮስን፡፡ አምስት ሰዎች ሞቱብን፣ የተረፍነውንም ተከተሉን። መቶ አለቃ ጠንክሮ ከመዋጋት ሌላ አማራጭ
እንደለለን ነገረን። ሌላ መንደር ለመሄድ በቂ ምግብ ወይም ጥይት የለንም፡፡ይሄን ጦርነት ካላሸነፍን ጫካው ውስጥ
መንከራተት ከዛም ማለቃችን ነው:: ስለዚህ ወደ ማጥቃት ገብተን መጀመሪያ ከሞቱት መሳሪያ አገኘን እና ተበተን::
በሁለተኛው ዙር እንደገና ተሰባስበን ማጥቃት ጀመርን::በመጨረሻ ከጠላቶቻችን በላይ ሐይል አግኝተን መበተን ቻልን:: የተኩስ እሩምታው በረደ፡፡ መንደሩ በእኛ ቁጥጥር ውስጥ ሆነ::
በድንገት ጥይቶችን በምሰበስብበት ወቅት የጥይት ዝናብ ወረደብን።
ሶስት ጊዜ እግሬ ላይ ተመትቼ ራሴን ስቼ ወደቅኩ። ሁለቱ ጥይቶች ገብተው ወጥተዋል አንዱ ግን እግሬ ውስጥ ቀረ::
በሚቀጥለው ቀን ስነቃ እግሮቼ ላይ ምስማር የተተከለ ይመስላል።
#ክፍል_አስራ_አምስት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
...ቅጠሎቹ አረንጓዴ ሲሆኑ ግንዱ ግን በጣም አርጅቷል። “ይሄን ስንነግራቸው ማንም አያምነንም” አለ አል ሃጂ።
የእራት ስዓት እየደረሰ ስለነበር ወደ ማዕከል መመለስ ነበረብን፡፡ ያን ምሽት ጓደኞቻችን ስለ ረጃጂም ህንጻዎች :
መኪናዎች እና ገበያው ነገርናቸው፡፡ ሁሉም ደስ ብሏቸው ማየት ፈለጉ። ማዕከሉም ይሄን በመረዳት በሳምንት አንድ ቀን የሽርሽር ፕሮግራም ተያዘልን፡፡
ቀስ በቀስ ወደ ትምህርት ተመለስን። ቀለል ያለ የትምህርት ስርዓት ነበር፡፡ ለሂሳብ መደመር፣ማባዛት እና ማካፈል ስንማር እንግሊዝኛ ደግሞ ምንባብ ማንበብ፣ ቃላቶችን ትርጉም ማወቅ
እና የእጅ ጽሁፍ እንማራለን። ብዙም አንከታተልም ; ትኩረታችን በትንሽ ነገር ይሰረቃል። በእርሳስ እንወጋጋላን
እንደባደባለን። “የናንተ ጥፋት አይደለም
ወደፊት ትስተካከላላችሁ' ይለናል መምህሩ።
ከምሳ በኋላ የጠረጴዛ ቴንስ ወይም እግር ኳስ እንጫወት ነበር። ለሊት ግን አስጨናቂ ነበር። በቅዥት እንባንናለን፣ በላብ እንጠመቃለን፣ ጩኸት እና ግድግዳ መደብደብ ነበር። ሰራተኞቹ
ይህን ስለሚያውቁ ጥበቃ ያደርጉልን ነበር።
የሴራሊዮን ዝናባማ ወቅት ከግንቦት እስከ ጥቅምት ሲሆን ሐምሌ፣ ነሐሴ እና መስከረም ደግሞ ከባድ ዝናብ ይኖራል።
ዝናቡ አንዳንዴ የጦርነቱን መጥፎ ትዝታዎች ይቀሰቅስብኛል።
የሰለጠንኩበት ቦታ እና የሞሪባ ሞት ትዝ ይለኛል። ሞሪባ በተኩስ እሩምታ ሲገደል መቅበር ቀርቶ ማልቀስ እንኳ አልቻልንም። አንድ ዛፍ ላይ አስጠግተነው በአፉ ደም እየደፈቀ ትተነው ሄድን።
ሲነጋ ሰራተኛዋ ብርድ ልብሱን መልሳ እያለበሰችኝ “ያንተ ጥፋት አይደለም በፍጹም! አይዞህ ትረሳዋለህ ይሻልሃል”
ትለኛለች፡፡
አንድ ቀን ረፋድ ላይ ቴንስ ስንጫወት የግቢው ሰራተኞች በሙሉ ይመለከቱን ነበር። አንድ ሰው ከኋላ ትከሻዬ ላይ ሲነካኝ ተሰማኝ ። ነርሷ ነበረች ። ነጭ ደምብ ልብስ እና ነጭ ኮፍያ ለብሳለች። ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር ፊት ለ ፊት ሳያት። ነጭ ጥርሷ ከጥቁር እና አንጸባራቂ ቆዳዋ ጋር ተጣምሮ ልዩ ውበት
ሰጥቷታል። ስትስቅ ደግሞ የበለጠ ውበቷ ይፈካል። ረዥም ናት፤ ትልልቅ አይኖች አሏት፡፡ ጠርሙስ ኮካ ኮላ ሰጥታኝ በሚያስፈልግህ ጊዜ ና እና እየኝ” ብላ ፈገግታ ሰጥታኝ ሄደች::
ከአል ሃጂ ጋር ጨዋታውን ትተን ወደ ውጭ ወጣን እና ኮካውን መጠጣት ጀመርን። “ወዳሃለች” እያለ አል ሃጂ ሊቀልድብኝ ሞከረ። ምንም አላልኩም::
እህ ትወዳታለህ እንዴ?” ብሎ ጠየቀኝ፡፡
“ እኔ አላውቅም:: ትልቅ ናት በዛ ላይ ነርሳችን ናት” አልኩ።
ማለት ሴቶችን ትፈራለህ?” አለ
“አንተ እንደምታስበው ወዳኝ አይመስለኝም” ብየ አል ሃጂን
ተመለከትኩት። የምለውን ነገር እያዳመጠ ይስቃል።
ኮካውን ጠጥተን እንደጨረስን አል ሃጂ ሄደ እኔ ግን ወደ ሆስፒታል ለመሄድ ወሰንኩ፡፡ በሩ ስደርስ ነርሷ ስልክ እያወራች አየኋት። እንድገባ እና እንድቀመጥ በእጇ ምልክት አሳየችኝ።
ወዲያው ስልኳን አቁማ ፈገግታ እያሳየችኝ ወንበሯን ወደ እኔ
አቀረበች፡፡ ስለ ጦርነቱ ጥያቄ ልትጠይቀኝ እንደሆነ ገመትኩ።
እሷ ግን በተረጋጋ መንፈስ “ ስምህ ማነው” ብላ ጠየቀችኝ፡፡ገረመኝ! ስሜን እንደምታውቀው እርግጠኛ ነበርኩ። “ስሜን ታውቂዋለሽ” ብየ በቁጣ መለስኩ።
“ ምን አልባት ላውቀው እችላለሁ ግን ስምህን እንድትነግረኝ እፈልጋለሁ?” አለች አይኗን እያፈጠጠች::
እሺ እሺ እስማይል” አልኩ፡፡
“ጥሩ ስም” አለች እራሷን እየነቀነቀች፡፡ “ የእኔ ስም አስቴር ነው። ጓደኛሞች እንሁን።”
“እርግጠኛ ነሽ ከእኔ ጋር ጓደኛ መሆን ትፈልጊያለሽ” አልኳት::ለተወሰነ ጊዜ ካሰበች በኋላ “እርግጠኛ ላልሆን እችላለሁ” አለች።
ምን ማለት እንዳለብኝ ስላላወቅኩ እና ማንንም ስለማመን ለተወሰነ ጊዜ ዝም አልኩ። እንዴት መትረፍ እና እራሴን
መንከባከብ እንዳለብኝ ብቻ ነው ነበር የተማርኩት። እንደ መቶ አለቃ ጃባቲ ያሉ ያመንኳቸው የታዘዝኳቸው ሰዎች እንኳ
ሰዎችን በተለይ አዋቂዎችን እንድጠራጠር አድርገውኛል::
የሰዎችን ሃሳብ መጠራጠር ከጀመርኩ ቆይቻለሁ። ሰዎች ጓደኛ የሚሆኑት አንዱ ሌላው ላይ ጥቅም ለማግኘት ነው ብየ አስብ ነበር፡፡ ስለዚህ ለነርሷ ምንም መልስ አልሰጠኋትም።
“ያንተ ነርስ ነኝ በቃ ይሄ ነው። ከእኔ ጋር ጓደኛ መሆን ከፈለክ ልትጠይቀኝ እና ላምንህ ይገባል” አለች። ተመሳሳይ ሃሳብ
ስለነበረን ፈገግ አልኩ። ፈገግታህ ያምራል” አለች። አፍሬ ቁጥብ ሆንኩ።
“ከከተማ እንዳመጣልህ የምትፈልገው ነገር አለ?” ብላ ጠየቀችኝ፡፡ መልስ አልሰጠሁም::
“ለዛሬ ይበቃናል” አለች፡፡
ከተወሰነ ቀን በኋላ ነርሷ ስጦታ ሰጠችኝ። የተጠቀለለ ነገር ነበር ምን ይሆን እያልኩ መክፈት ጀመርኩ። ልክ እንዳየሁት በደስታ ተነስቼ አቀፍኳት። “ጓደኛ ካልሆን ለምን ይሄን ማዳመጫ እና ካሴት አመጣሽልኝ? ራፕ ሙዚቃ እንደምወድ እንዴት አወቅሽ?”
“እባክህ ተቀመጥ” አለች። የጆሮ ማዳመጫውን አደረኩ
D.M.C የዲ.ኤም.ሲ ሙዚቃ ነበር የምሰማው “It's like that and that the Way it is...” እንደዛ ነው እንደነገሩ” ራሴን ማንቀሳቀስ ጀመርኩ።አስቴር የጆሮ ማዳመጫውን ከጆሮዬ አውጥታ “አንተ ሙዚቃ ስታዳምጥ እኔ ልመረምርህ ነው”
አለች። ተስማማሁ። ምላሴን ፣ አይኔን አየች ከዛ እግሬን ስታይ ጠባሳ ነበረኝ። “ይሄ ጠባሳ እንዴት ወጣብህ?”
“በጥይት ተመትቼ ቆስየ ነው” እላለሁ በቀላሉ።
ፊቷ በሃዘን ተሞላ “ምን እንደሆንክ ምን እንደሚሰማህ ከነገርከኝ መድሃኒት ላዝልህ እችላለሁ” አለች። ሁሉንም
ነገርኳት፡፡ እንዴት በጥይት እንደተመታሁ፣
ስንት ጊዜ እንደተመታሁ እና ከዛ ምን እንዳደረኩ ነገርኳት። ልነግራት ግን
ፈልጌ አልነበረም፡፡ አስቃቂውን የጦርነቱን ክስተት ስነግራት መጠየቅ ታቆማለች ብዬ እንጂ። እሷ ግን በጥንቃቄ ታዳምጣለች። የትናንቱን ታሪኬን ማስታወስ ስጀምር አንገቴን ደፋሁ።
በበጋ ወቅት ስለነበረው ጦርነት ነገርኳት። ምግብ እና ጥይት ያጠረን አስቸጋሪ ወቅት ነበር። ሌላ መንደር ማጥቃት ነበረብን።ከትንሽ ስለላ በኋላ የሶስት ቀን ጉዞ ወደ ሚጠይቅ አንድ ሰፈር ሄድን። እቅዳችን ምግብ እና ጥይት ይዞ መምጣት ሳይሆን የምናጠቃውን ሰፈር ወደ ዋና ማዕከል መቀየር ነበር። ያለን
መሳሪያ እና ምግብ ይዘን ወጣን። ቦታው ደርሰን ለደፈጣ ውጊያ ስንዘጋጅ መንደሩ ባዶ መሆኑን ተገነዘብን። ከስዓት በኋላ
አምስት ታጣቂዎች መጥተው ባልዲ ይዘው ወደ ወንዙ ወረዱ..ገና መጠርጠር ስንጀምር ከኋላ ተኩስ ተከፈተብን። ለሊቱን ሙሉ ተታኮስን፡፡ አምስት ሰዎች ሞቱብን፣ የተረፍነውንም ተከተሉን። መቶ አለቃ ጠንክሮ ከመዋጋት ሌላ አማራጭ
እንደለለን ነገረን። ሌላ መንደር ለመሄድ በቂ ምግብ ወይም ጥይት የለንም፡፡ይሄን ጦርነት ካላሸነፍን ጫካው ውስጥ
መንከራተት ከዛም ማለቃችን ነው:: ስለዚህ ወደ ማጥቃት ገብተን መጀመሪያ ከሞቱት መሳሪያ አገኘን እና ተበተን::
በሁለተኛው ዙር እንደገና ተሰባስበን ማጥቃት ጀመርን::በመጨረሻ ከጠላቶቻችን በላይ ሐይል አግኝተን መበተን ቻልን:: የተኩስ እሩምታው በረደ፡፡ መንደሩ በእኛ ቁጥጥር ውስጥ ሆነ::
በድንገት ጥይቶችን በምሰበስብበት ወቅት የጥይት ዝናብ ወረደብን።
ሶስት ጊዜ እግሬ ላይ ተመትቼ ራሴን ስቼ ወደቅኩ። ሁለቱ ጥይቶች ገብተው ወጥተዋል አንዱ ግን እግሬ ውስጥ ቀረ::
በሚቀጥለው ቀን ስነቃ እግሮቼ ላይ ምስማር የተተከለ ይመስላል።
የጦር ሃኪሙ የሆነ ነገር ወጋኝ እና ደነዘዝኩ።
ሌሎች ጓደኞቼ እጆቼን ሲይዙ አፌ ላይ ጨርቅ ተደረገ። ቀጥሎ ሃኪሙ በመቀስ ጥይቷን አወጣት:: ከሶስት ሳምንታት በኋላ ነበር የተሻለኝ፡፡ ሃኪሙ ቁስሌን እያጠበ ደጋግሞ “እድለኛ ነህ”
ይለኝ ነበር። ጦርነትን ለማሸነፍ ወይም ከጦርነት ለመትረፍ ጥሩ ስልጠና ወይም ድፍረት ጀግንነት እንጂ እድል ቦታ ያለው
አይመስለኝም ነበር፡፡ ቆይቶ ግን ገባኝ:: ብዙ መከራዎችን በሚገርም ተዓምር ተረፍኩ። ሞት ማይደርስብኝ የማይነካኝ
ይመስለኝ ጀመር።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
ሌሎች ጓደኞቼ እጆቼን ሲይዙ አፌ ላይ ጨርቅ ተደረገ። ቀጥሎ ሃኪሙ በመቀስ ጥይቷን አወጣት:: ከሶስት ሳምንታት በኋላ ነበር የተሻለኝ፡፡ ሃኪሙ ቁስሌን እያጠበ ደጋግሞ “እድለኛ ነህ”
ይለኝ ነበር። ጦርነትን ለማሸነፍ ወይም ከጦርነት ለመትረፍ ጥሩ ስልጠና ወይም ድፍረት ጀግንነት እንጂ እድል ቦታ ያለው
አይመስለኝም ነበር፡፡ ቆይቶ ግን ገባኝ:: ብዙ መከራዎችን በሚገርም ተዓምር ተረፍኩ። ሞት ማይደርስብኝ የማይነካኝ
ይመስለኝ ጀመር።
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_አስራ_ስድስት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
ይሄን ነግሬያት ከሆስፒታሉ ለመውጣት ተነሳሁ። አስቴር ግን “በኮንናውት ሆስፒታል ሙሉ ምርመራ እንድታደርግ
ሁኔታዎችን አመቻቻለሁ።” ብላ ላፍታ ዝም ብላ ከቆየች በኋላ ሙዚቃ ማዳመጫው ከእኔ ጋር ይቆይ ሌሎች እንዲቀኑብህ
እና እንዲሰርቁህ አያስፈልግም፡፡ በፈለከው ቀን መጥተህ ማዳመጥ ትችላለህ። ሁሌም እኔ ከዚህ ነኝ” አለች። ሙዚቃ ማዳመጫውን ወርውሬ ወጣሁ።
አንድ ቀን ከስዓት አስቴር ከስራ እረፍት ብትሆንም ከሁለት ሌላ ሰዎችጋር በነጭ ቶዮታ መጣች። አንዱ ሰው ሹፌር ሲሆን
ሌላው ግን የ ጦርነት ጋር የተገናኙ ህጻናት ወይም Children Associated with War የመስክ ሰራተኛ ነበር። ድርጅቱ ከ ዩኒሴፍ እና ሌሎች መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር የሚሰራ የካቶሊክ ድርጅት ነበር።
“ ወደ ሆስፒታል ሂደን ከተመረመርክ በኋላ ከተማ ሽርሽር ትሄዳለህ።” አስቴር በደስታ ምን ትላለህ ብላ ጠየቀችኝ፡፡
“እሺ” ብየ ተስማማሁ። ደስ ብሎኛል።”ጓደኛየ አል ሃጂ መምጣት ይችላል?” ብየ ጠየቅኩ።
“ይችላል” ስትል እንደምጠይቃት የጠበቀች ይመስላል።ወደ ፍሪ ታውን መንቀሳቀስ ስንጀምር የመስክ ሰራተኛው
“ ስሜ ለስሊ ይባላል፤ ስላገኘሁህ ደስ ብሎኛል” ብሎ ተዋወቅን።ወደ መሐል ከተማው ስንደርስ አስቴር እጆቿን እየጠቆመች ፖስታ ቤት፣ ሱቆችን፣ የተባባሩት መንግስታት ድርጂት
ህንጻዎችን እና የጥጥ ዛፉን አሳየችኝ። በከተማው ሁሌም እደነቃለሁ። በስራ የተጠመዱ ሰዎች ሲጣደፉ ሲወጡ ሲወርዱ የነጋዴዎች የግዙኝ ጩኧት ደግሞ ልዩ ድምፅ ይሰጣል።
ዶክተሩ የቆሰለ ወይም በጥይት የተወጋ ሰውነቴን እየነካ እና እየጨበጠ “የሚሰማህ ነገር አለ” እያለ ደጋግሞ ይጠይቀኝ ነበር፡፡መናደድ ስጀምር ጨርሰሃል አለኝ፡፡ ልብሴን ለብሼ አስቴር ፣
ለስሊ እና አል ሃጂ ወደ ሚገኙበት መቆያ ክፍል ሄድኩ::ተያይዘን ወደ ገበያው ሄድን። አስቴር ለ አል ሃጂ የስፖርት
ማሊያ ስትገዛለት ለስሊ ደግሞ ለእኔ የ ቦብ ማርሌን ኤክሶዶስ (ስደት) የሚለውን አልበም ገዛልኝ፡፡ አል ሃጂ ማሊያውን
ወዲያው ለበሰው:: ማሊያው የሃገሪቱን ብሔራዊ ሰንደቃላማ ማለትም አረንጓዴ፣ ነጭ እና ሰማያዊ ቀለማቶችን ይዟል።
አስቴር ለሁላችንም ኮካ ኮላ ገዛችልን። ለስለ እኔ እና ሌሎች ልጆችን ለማገዝ እንደተመደበ እና ዋና ስራው እኛ ከማገገሚያው በኋላ ለሚኖረን ህይወት ነገሮችን ማመቻቸት ነው።
በሚቀጥለው ቀን ወደ ከተማ ተመልሰን እኔ ሆስፒታል ሄድኩ። አስቴር ራሴን እያሻሸች “ መልካም ዜና ነው። ውጤትህ
መጥቷል። ዶክተሩ ለክፉ የሚሰጥ ህመም እንደሌለብህ አረጋግጧል። ለበለጠ እርግጠኝነት የተወሰኑ መድሃኒቶችን ትወስድ እና ዳግም ምርመራ ይደረግልሃል” አለች። ምንም
አላልኩም ! እሷ ግን ካሴት እና ማዳመጫውን ሰጠችኝ። አስቴርን እየለመድኳት ስመጣ ስለ ብዙ ነገር ማውራት ጀመርን፡፡በተለይ ግን ስለ ሙዚቃ ቦብ ማርሌ እና ራን ዲ.
ኤም.ሲ፡፡ ለስሊ በሳምንት ሁለት ጊዜ ይመጣ ነበር። ስለ ራስ ተፈሪያኒዝም ማውራት ይወዳል። እኔም #የኢትዮጵያ ታሪክ ደስ ይለኛል በተለይ ንግስት ሳባ እና ንጉስ ሰለሞን የተገናኙበት ታሪክ
ይገርመኛል። የተጓዙት ረዥሙ ጉዞ ፣ የመረጡት ቦታ እና ለመድረስ ያሳዩት ፅናት ሁሌም ይገርመኛል። ከህይወቴ ጋርም ለማገናኘት እጥራለሁ፡፡ የእኔ የህይወት ሩጫ እንደ እነሱ ትርጉም ያለው እና ደስታ የሞላበት እንዲሆን እመኛለሁ።
አንድ ምሽት አስቴር ቤቷ ወሰዳ እራት ጋበዘችኝ፡፡ ከእራት በኋላ ወደ ከተማ ወጥተን መናፈስ ጀመርን። ራውዶን መንገድ ጫፍ ወዳለ የባህር ዳርቻ ሄድን። ጨረቃ በድምቀት ወጥታ ነበር እና ደርቻው ላይ ሁነን መመልከት ጀመርን፡
ልጅ እያለሁ በጨረቃ ውስጥ የተለያየ ቅርፆችን እንመለከት እንደነበር ለ
አስቴር ነገርኳት። ገረማት። ጨረቃዋን እያየን የያዘችው ቅርፅ ምን እንደሆነ መገመት ጀመርን።
ልጅ እያለሁ አያቴ አስተውሎ ለሚያይ እና ለሚያዳምጥ ሰው ሰማይ ይናገራል ትል ነበር፡፡ በሰማይ ሁሌም የጥያቄዎቻችን
መልስ እና የነገሮች ምክንያት ይገለፃል። የእያንዳንዱ ስቃይ፣ ጉዳት፣ ደስታ እና ግራ መጋባት መንስዔ ይነገራል፡፡” ያ ለሊት ሰማዩ እንዲያወራኝ ፈለኩ።
ከአምስት ወር የቤኒን ማገገሚያ ቆይታ በኋላ አንድ ቀን ዓለት ድንጋይ ላይ ተክዤ ተቀምጬ እያለሁ አስቴር አየችኝ። ምንም
ሳትናገር መጥታ ከጎኔ ተቀመጠች። በሰለለ ድምፅ “ ከዚህ በኋላ የምኖርለት ምክንያት ያለ አልመስለኝ እያለ ነው” አልኩ።” ቤተሰብ የለኝም። እኔ ብቻ ነው የቀረሁት። የልጅነት ታሪኬን እንኳ የሚናገር የለም::”
አስቴር እጆቹዋን ወደ እኔ ልካ ጎትታ አስጠጋችኝ እና አቅፋ
“እኔን እንደ ቤተሰብህ አስበኝ፤ እንደ እህት ” አለች:: ግን እህት እኮ የለኝም”
አሁን አለህ፡፡ የአዲስ ህይወት ገፀ በረከት ነው። የተለያዩ የቤተሰብ አባላትን ማፍራት ትችላለህ።” ብላ አየችኝ፡፡
“እሺ! እህቴ መሆን ትችያለሽ ለጊዜው።”
“ይሁን ስለዚህ ነገ ጊዚያዊ እህትህን ለማየት ትመጣለህ አይደል።”
“እሺ!”
በሚቀጥለው ቀን አስቴር ወደ ማዕከሉ የሚመጡ ጎብኚዎች እንዳሉ ነገረችኝ። ሰራተኞቹ የተሰጥዎ ውድድር እንድናደርግ ጠየቁን፡፡ የምንችለውን ማንኛውንም አይነት ነገር እንድናቀርብ
ነበር የተፈለገው።
ሬጌ ሙዚቃህን ለምን አትዘፍንም” ብላ አስቴር ሃሳብ አቀረበች።
• የሼክስፒርን ቃለ ተውኔትን ባቀርብስ”
“እሺ ትንሽ ሙዚቃ ብትጨምር ጥሩ ይመስለኛል” አለች
እጆችዋን ትከሻየ ላይ አደርጋ። ወድጃታለሁ ግን መውደዱን አላሳያትም:: ስታቅፈኝ ቀስ ብየ ከእቅፏ እወጣለሁ፡፡ ስትሄድ ግን አያታለሁ። ከትምህርት በኋላ ሩጬ እሷን ላይ እሄዳለሁ።ጓደኞቼ ማቡ እና አል ሃጂ “ የሴት ጓደኛህ መጣች እስማኤል” እያሉ ይቀልድብኛል፡፡
ጎብኚዎቹ ከ አውሮፓ ኮሚሽን፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ሌሎች መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጂቶች የተውጣጡ ናቸው። ሙሉ ልብስ ከነከራባቱ ለብሰዋል። እርስበርሳቸው
ስላምታ ከተለዋወጡ በኋላ ማዕከሉን እየዞሩ ቃኙ። በኋላ ለተሰጥኦ ውድድሩ በሚገባ ወደ ተዘጋጀው ወደ ምግብ አዳራሽ ገቡ። የማዕከሉ ዳሬክተር አቶ ካማራ የመክፈቻ ንግግር ካደረጉ
በኋላ ውድድሩ ቀጠለ። ተረቶች፣ አስፈሪ ታሪኮች እና የባህል ጭፈራዎች ቀረቡ። እኔ ከጁሊየስ ቄሳር የተወሰነ ቃለ ተውኔት
ካቀረብኩ በኋላ አንድ የሂፕ ሆፕ ሙዚቃ ተጫወትኩ።ሙዚቃው ስለ አንድ ታዳጊ ወታደር ትንሳኤ ሲሆን በአስቴር
የሞራል ድጋፍ እራሴ የፃፍኩት ነው::
ከውድድሩ በኋላ በማዕከሉ ታዋቂ ሆንኩ። የማዕከሉ ዳሬክተር አቶ ካማራ ቢሯቸው ጠርተው “ አንተ እና ጓደኞችህ የእውነት ጎብኚዎችን አስደምማችኋል። አሁን ታዳጊዎች ማገግም እንደሚችሉ አውቀዋል።” አሉ። ወደፊት እንደገና የማቅረብ እድሉ እንዳለኝ ሳውቅ በጣም ደስ አለኝ፡፡ አቶ ካማራ ደግሞ ከእኔ
በላይ በከፍተኛ ስሜት ላይ ነበሩ።
የማዕከሉ ቃል አቀባይ ብትሆን ምን ይመስልሃል?” ብለው ጠየቁኝ፡፡
“ምን! ምንድን ነው ምሰራው ወይም የምናገረውስ?”አልኩ።
“ በመጀመሪያ ስለ ታዳጊ ወታደሮች ዝግጅት በሚኖርበት ጊዜ የምታነበውን ነገር እንፅፍልሃለን። ስራውን ከለመድከው በኋላ ፀ የምታቀርበውን ንግግር እራስህ ልታዘጋጅ ትችላለህ” አሉኝ::
ሳምንት ሳይቆይ በታዳጊ ወታደርነት እና እንዴት መቆም አለበት በሚሉ ሃሳቦች ላይ ንግግር አደረኩ። “ማገገም እንችላለን ብየ እራሴን ምሳሌ በማድረግ ህፃናት ከችግሩ መውጣት
#ክፍል_አስራ_ስድስት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
ይሄን ነግሬያት ከሆስፒታሉ ለመውጣት ተነሳሁ። አስቴር ግን “በኮንናውት ሆስፒታል ሙሉ ምርመራ እንድታደርግ
ሁኔታዎችን አመቻቻለሁ።” ብላ ላፍታ ዝም ብላ ከቆየች በኋላ ሙዚቃ ማዳመጫው ከእኔ ጋር ይቆይ ሌሎች እንዲቀኑብህ
እና እንዲሰርቁህ አያስፈልግም፡፡ በፈለከው ቀን መጥተህ ማዳመጥ ትችላለህ። ሁሌም እኔ ከዚህ ነኝ” አለች። ሙዚቃ ማዳመጫውን ወርውሬ ወጣሁ።
አንድ ቀን ከስዓት አስቴር ከስራ እረፍት ብትሆንም ከሁለት ሌላ ሰዎችጋር በነጭ ቶዮታ መጣች። አንዱ ሰው ሹፌር ሲሆን
ሌላው ግን የ ጦርነት ጋር የተገናኙ ህጻናት ወይም Children Associated with War የመስክ ሰራተኛ ነበር። ድርጅቱ ከ ዩኒሴፍ እና ሌሎች መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር የሚሰራ የካቶሊክ ድርጅት ነበር።
“ ወደ ሆስፒታል ሂደን ከተመረመርክ በኋላ ከተማ ሽርሽር ትሄዳለህ።” አስቴር በደስታ ምን ትላለህ ብላ ጠየቀችኝ፡፡
“እሺ” ብየ ተስማማሁ። ደስ ብሎኛል።”ጓደኛየ አል ሃጂ መምጣት ይችላል?” ብየ ጠየቅኩ።
“ይችላል” ስትል እንደምጠይቃት የጠበቀች ይመስላል።ወደ ፍሪ ታውን መንቀሳቀስ ስንጀምር የመስክ ሰራተኛው
“ ስሜ ለስሊ ይባላል፤ ስላገኘሁህ ደስ ብሎኛል” ብሎ ተዋወቅን።ወደ መሐል ከተማው ስንደርስ አስቴር እጆቿን እየጠቆመች ፖስታ ቤት፣ ሱቆችን፣ የተባባሩት መንግስታት ድርጂት
ህንጻዎችን እና የጥጥ ዛፉን አሳየችኝ። በከተማው ሁሌም እደነቃለሁ። በስራ የተጠመዱ ሰዎች ሲጣደፉ ሲወጡ ሲወርዱ የነጋዴዎች የግዙኝ ጩኧት ደግሞ ልዩ ድምፅ ይሰጣል።
ዶክተሩ የቆሰለ ወይም በጥይት የተወጋ ሰውነቴን እየነካ እና እየጨበጠ “የሚሰማህ ነገር አለ” እያለ ደጋግሞ ይጠይቀኝ ነበር፡፡መናደድ ስጀምር ጨርሰሃል አለኝ፡፡ ልብሴን ለብሼ አስቴር ፣
ለስሊ እና አል ሃጂ ወደ ሚገኙበት መቆያ ክፍል ሄድኩ::ተያይዘን ወደ ገበያው ሄድን። አስቴር ለ አል ሃጂ የስፖርት
ማሊያ ስትገዛለት ለስሊ ደግሞ ለእኔ የ ቦብ ማርሌን ኤክሶዶስ (ስደት) የሚለውን አልበም ገዛልኝ፡፡ አል ሃጂ ማሊያውን
ወዲያው ለበሰው:: ማሊያው የሃገሪቱን ብሔራዊ ሰንደቃላማ ማለትም አረንጓዴ፣ ነጭ እና ሰማያዊ ቀለማቶችን ይዟል።
አስቴር ለሁላችንም ኮካ ኮላ ገዛችልን። ለስለ እኔ እና ሌሎች ልጆችን ለማገዝ እንደተመደበ እና ዋና ስራው እኛ ከማገገሚያው በኋላ ለሚኖረን ህይወት ነገሮችን ማመቻቸት ነው።
በሚቀጥለው ቀን ወደ ከተማ ተመልሰን እኔ ሆስፒታል ሄድኩ። አስቴር ራሴን እያሻሸች “ መልካም ዜና ነው። ውጤትህ
መጥቷል። ዶክተሩ ለክፉ የሚሰጥ ህመም እንደሌለብህ አረጋግጧል። ለበለጠ እርግጠኝነት የተወሰኑ መድሃኒቶችን ትወስድ እና ዳግም ምርመራ ይደረግልሃል” አለች። ምንም
አላልኩም ! እሷ ግን ካሴት እና ማዳመጫውን ሰጠችኝ። አስቴርን እየለመድኳት ስመጣ ስለ ብዙ ነገር ማውራት ጀመርን፡፡በተለይ ግን ስለ ሙዚቃ ቦብ ማርሌ እና ራን ዲ.
ኤም.ሲ፡፡ ለስሊ በሳምንት ሁለት ጊዜ ይመጣ ነበር። ስለ ራስ ተፈሪያኒዝም ማውራት ይወዳል። እኔም #የኢትዮጵያ ታሪክ ደስ ይለኛል በተለይ ንግስት ሳባ እና ንጉስ ሰለሞን የተገናኙበት ታሪክ
ይገርመኛል። የተጓዙት ረዥሙ ጉዞ ፣ የመረጡት ቦታ እና ለመድረስ ያሳዩት ፅናት ሁሌም ይገርመኛል። ከህይወቴ ጋርም ለማገናኘት እጥራለሁ፡፡ የእኔ የህይወት ሩጫ እንደ እነሱ ትርጉም ያለው እና ደስታ የሞላበት እንዲሆን እመኛለሁ።
አንድ ምሽት አስቴር ቤቷ ወሰዳ እራት ጋበዘችኝ፡፡ ከእራት በኋላ ወደ ከተማ ወጥተን መናፈስ ጀመርን። ራውዶን መንገድ ጫፍ ወዳለ የባህር ዳርቻ ሄድን። ጨረቃ በድምቀት ወጥታ ነበር እና ደርቻው ላይ ሁነን መመልከት ጀመርን፡
ልጅ እያለሁ በጨረቃ ውስጥ የተለያየ ቅርፆችን እንመለከት እንደነበር ለ
አስቴር ነገርኳት። ገረማት። ጨረቃዋን እያየን የያዘችው ቅርፅ ምን እንደሆነ መገመት ጀመርን።
ልጅ እያለሁ አያቴ አስተውሎ ለሚያይ እና ለሚያዳምጥ ሰው ሰማይ ይናገራል ትል ነበር፡፡ በሰማይ ሁሌም የጥያቄዎቻችን
መልስ እና የነገሮች ምክንያት ይገለፃል። የእያንዳንዱ ስቃይ፣ ጉዳት፣ ደስታ እና ግራ መጋባት መንስዔ ይነገራል፡፡” ያ ለሊት ሰማዩ እንዲያወራኝ ፈለኩ።
ከአምስት ወር የቤኒን ማገገሚያ ቆይታ በኋላ አንድ ቀን ዓለት ድንጋይ ላይ ተክዤ ተቀምጬ እያለሁ አስቴር አየችኝ። ምንም
ሳትናገር መጥታ ከጎኔ ተቀመጠች። በሰለለ ድምፅ “ ከዚህ በኋላ የምኖርለት ምክንያት ያለ አልመስለኝ እያለ ነው” አልኩ።” ቤተሰብ የለኝም። እኔ ብቻ ነው የቀረሁት። የልጅነት ታሪኬን እንኳ የሚናገር የለም::”
አስቴር እጆቹዋን ወደ እኔ ልካ ጎትታ አስጠጋችኝ እና አቅፋ
“እኔን እንደ ቤተሰብህ አስበኝ፤ እንደ እህት ” አለች:: ግን እህት እኮ የለኝም”
አሁን አለህ፡፡ የአዲስ ህይወት ገፀ በረከት ነው። የተለያዩ የቤተሰብ አባላትን ማፍራት ትችላለህ።” ብላ አየችኝ፡፡
“እሺ! እህቴ መሆን ትችያለሽ ለጊዜው።”
“ይሁን ስለዚህ ነገ ጊዚያዊ እህትህን ለማየት ትመጣለህ አይደል።”
“እሺ!”
በሚቀጥለው ቀን አስቴር ወደ ማዕከሉ የሚመጡ ጎብኚዎች እንዳሉ ነገረችኝ። ሰራተኞቹ የተሰጥዎ ውድድር እንድናደርግ ጠየቁን፡፡ የምንችለውን ማንኛውንም አይነት ነገር እንድናቀርብ
ነበር የተፈለገው።
ሬጌ ሙዚቃህን ለምን አትዘፍንም” ብላ አስቴር ሃሳብ አቀረበች።
• የሼክስፒርን ቃለ ተውኔትን ባቀርብስ”
“እሺ ትንሽ ሙዚቃ ብትጨምር ጥሩ ይመስለኛል” አለች
እጆችዋን ትከሻየ ላይ አደርጋ። ወድጃታለሁ ግን መውደዱን አላሳያትም:: ስታቅፈኝ ቀስ ብየ ከእቅፏ እወጣለሁ፡፡ ስትሄድ ግን አያታለሁ። ከትምህርት በኋላ ሩጬ እሷን ላይ እሄዳለሁ።ጓደኞቼ ማቡ እና አል ሃጂ “ የሴት ጓደኛህ መጣች እስማኤል” እያሉ ይቀልድብኛል፡፡
ጎብኚዎቹ ከ አውሮፓ ኮሚሽን፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ሌሎች መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጂቶች የተውጣጡ ናቸው። ሙሉ ልብስ ከነከራባቱ ለብሰዋል። እርስበርሳቸው
ስላምታ ከተለዋወጡ በኋላ ማዕከሉን እየዞሩ ቃኙ። በኋላ ለተሰጥኦ ውድድሩ በሚገባ ወደ ተዘጋጀው ወደ ምግብ አዳራሽ ገቡ። የማዕከሉ ዳሬክተር አቶ ካማራ የመክፈቻ ንግግር ካደረጉ
በኋላ ውድድሩ ቀጠለ። ተረቶች፣ አስፈሪ ታሪኮች እና የባህል ጭፈራዎች ቀረቡ። እኔ ከጁሊየስ ቄሳር የተወሰነ ቃለ ተውኔት
ካቀረብኩ በኋላ አንድ የሂፕ ሆፕ ሙዚቃ ተጫወትኩ።ሙዚቃው ስለ አንድ ታዳጊ ወታደር ትንሳኤ ሲሆን በአስቴር
የሞራል ድጋፍ እራሴ የፃፍኩት ነው::
ከውድድሩ በኋላ በማዕከሉ ታዋቂ ሆንኩ። የማዕከሉ ዳሬክተር አቶ ካማራ ቢሯቸው ጠርተው “ አንተ እና ጓደኞችህ የእውነት ጎብኚዎችን አስደምማችኋል። አሁን ታዳጊዎች ማገግም እንደሚችሉ አውቀዋል።” አሉ። ወደፊት እንደገና የማቅረብ እድሉ እንዳለኝ ሳውቅ በጣም ደስ አለኝ፡፡ አቶ ካማራ ደግሞ ከእኔ
በላይ በከፍተኛ ስሜት ላይ ነበሩ።
የማዕከሉ ቃል አቀባይ ብትሆን ምን ይመስልሃል?” ብለው ጠየቁኝ፡፡
“ምን! ምንድን ነው ምሰራው ወይም የምናገረውስ?”አልኩ።
“ በመጀመሪያ ስለ ታዳጊ ወታደሮች ዝግጅት በሚኖርበት ጊዜ የምታነበውን ነገር እንፅፍልሃለን። ስራውን ከለመድከው በኋላ ፀ የምታቀርበውን ንግግር እራስህ ልታዘጋጅ ትችላለህ” አሉኝ::
ሳምንት ሳይቆይ በታዳጊ ወታደርነት እና እንዴት መቆም አለበት በሚሉ ሃሳቦች ላይ ንግግር አደረኩ። “ማገገም እንችላለን ብየ እራሴን ምሳሌ በማድረግ ህፃናት ከችግሩ መውጣት
👍3😁1
እንዳለባቸው እና እድሉን ካገኙ መውጣት እንደሚችሉ በአፅንዖት ተናገርኩ።
የስድስተኛ ወር የማገገሚያው ቆይታን በማገባደድ ላይ እያለሁ የልጅነት ጎደኛዬ መሐመድ ወደ ማዕከሉ መጣ።
ለመጨረሻ ጊዜ ያየሁት ሞግዊሞን ለቅቄ ከቶሊ እና ጅንየር ጋር ወደ ማትሩ ጆንግ የሙዚቃ ውድድር ለመሳትፍ በሄድንበት ወቅት ነበር። ያኔ ከአባቱ ጋር የሳር ቤታቸውን እያደሱ ስለነበር
መምጣት አልቻለም፡፡ ሁሌም ምን ሁኖ ይሆን ብየ አስብ ነበር::ነገር ግን እንደገና አየዋለሁ ብየ አስቤ አላውቅም::
ጠይም ቀጫጫ ልጅ እየሮጠ መጥቶ
አስታወስከኝ” ካለ በኋላ መደነስ መዝፈን ጀመረ:: መዶሻው መጣልህ” የሚለውን ሲዘፍን አብሬው መዝፈን ጀመርኩ።
አብረን ከዳነስን በኋላ ተቃቀፍን። ስለልጅነታችን መጫወት ስንጀምር “ አንዳንዴ ያ መልካም ጊዜ በሙዚቃ ውድድሮች ተሳትፈን የምንደንሰው፣ አዳዲስ የዳንስ አይነቶች የምንለማመደው እና ኳሷን ማየት እስከሚሳነን እግር ኳስ የምንጫወተው ትዝ ይለኛል..ከረጅም ጊዜ በኋላ ይመስላል።አይገርምም? "
“ይገርማል”
በሰባተኛው ወር መጀመሪያ ለስሊ አስጠርቶኝ በማዕከሉ አንድ ክፍል ተገናኘን፡፡ ሳገኘው ፊቱ የሃዘን እና ደስታ ስሜቶች በመፈራረቅ ይነበቡበታል...
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
የስድስተኛ ወር የማገገሚያው ቆይታን በማገባደድ ላይ እያለሁ የልጅነት ጎደኛዬ መሐመድ ወደ ማዕከሉ መጣ።
ለመጨረሻ ጊዜ ያየሁት ሞግዊሞን ለቅቄ ከቶሊ እና ጅንየር ጋር ወደ ማትሩ ጆንግ የሙዚቃ ውድድር ለመሳትፍ በሄድንበት ወቅት ነበር። ያኔ ከአባቱ ጋር የሳር ቤታቸውን እያደሱ ስለነበር
መምጣት አልቻለም፡፡ ሁሌም ምን ሁኖ ይሆን ብየ አስብ ነበር::ነገር ግን እንደገና አየዋለሁ ብየ አስቤ አላውቅም::
ጠይም ቀጫጫ ልጅ እየሮጠ መጥቶ
አስታወስከኝ” ካለ በኋላ መደነስ መዝፈን ጀመረ:: መዶሻው መጣልህ” የሚለውን ሲዘፍን አብሬው መዝፈን ጀመርኩ።
አብረን ከዳነስን በኋላ ተቃቀፍን። ስለልጅነታችን መጫወት ስንጀምር “ አንዳንዴ ያ መልካም ጊዜ በሙዚቃ ውድድሮች ተሳትፈን የምንደንሰው፣ አዳዲስ የዳንስ አይነቶች የምንለማመደው እና ኳሷን ማየት እስከሚሳነን እግር ኳስ የምንጫወተው ትዝ ይለኛል..ከረጅም ጊዜ በኋላ ይመስላል።አይገርምም? "
“ይገርማል”
በሰባተኛው ወር መጀመሪያ ለስሊ አስጠርቶኝ በማዕከሉ አንድ ክፍል ተገናኘን፡፡ ሳገኘው ፊቱ የሃዘን እና ደስታ ስሜቶች በመፈራረቅ ይነበቡበታል...
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍1
#የፈሪ_ሰው_ጸሎት
አምላክ ሆይ .
ይግባኝ ዐለኝና አቤት የምልበት
በአርባ አራት ጾሜ ሕግን 'ምሽርበት።
ለምን? የሚል ሐሳብ . . .
በመሸነፍ ብእር ልብ ወለድ ተደርሶ
ይጠይቃል ልቤ ከዙፋንኽ ደርሶ።
እዚኽ . . .
ሕግን እያወጣ ደንብ እያረቀቀ
ሕዝብ እያስከበረ እራሱ እየናቀ፣
ይበይንብኻል . . .!
አያድን ከቅጣት ሕግን ያላወቀ።
( . . . እያለ. . .)
( ፈተና ፩ )
ሠፊው የ'ኔ ዓለም . . .
ስልቻ ላይሞላ ሠርክ ፍዳ ኾነ
ሆድ የሚሉት ዋሻ ለግብሩ ታመነ ፣
ድንጋይን ከዳቦ እያፎካከረ
ኅሊናን ረስቶ ተገዛ ፣ታሰረ።
( ፈተና ፪ )
መከራዬ ኹሉ ዕንገት እያስደፋኝ
መንገዴ በሙሉ 0ጉኖ እያፋፋኝ ፣
ጠረጠርኩኝና ...
በኾነው በቀኑ መድረስኽን ረሳኹ ፤
በማወቅ ጉጉቴ . . .
ከመቅደስ ከፍታ ለመውደቅ ተነሣኹ።
( ፈተና ፫ )
ነባዊ . . .
ልባዊ . .
ሕያዊ . . .
መገመት ጀመሩ ፤ አንሰው ኮሰሱና
እሩጫው ዐየለ ፤ መስገድ እረሱና ፣
ሙዳይ መስፈራዬ አስገምቶኝ ከ'ኔ
ገዛኹ ፣ተገዛኹኝ ፤ በምድራዊው ቅኔ።
እናም . .
ልቤ ቃልን ስቶ
ለሥጋ ተገዝቶ
በዓለም ተመርቶ።
በሰው መኾን ግብር
አልችል ካለች ነፍሴ ፈተናውን ማለፍ፤
ይግባኝ ባሉት ብሂል ይቺ ጽዋ ትለፍ።
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
አምላክ ሆይ .
ይግባኝ ዐለኝና አቤት የምልበት
በአርባ አራት ጾሜ ሕግን 'ምሽርበት።
ለምን? የሚል ሐሳብ . . .
በመሸነፍ ብእር ልብ ወለድ ተደርሶ
ይጠይቃል ልቤ ከዙፋንኽ ደርሶ።
እዚኽ . . .
ሕግን እያወጣ ደንብ እያረቀቀ
ሕዝብ እያስከበረ እራሱ እየናቀ፣
ይበይንብኻል . . .!
አያድን ከቅጣት ሕግን ያላወቀ።
( . . . እያለ. . .)
( ፈተና ፩ )
ሠፊው የ'ኔ ዓለም . . .
ስልቻ ላይሞላ ሠርክ ፍዳ ኾነ
ሆድ የሚሉት ዋሻ ለግብሩ ታመነ ፣
ድንጋይን ከዳቦ እያፎካከረ
ኅሊናን ረስቶ ተገዛ ፣ታሰረ።
( ፈተና ፪ )
መከራዬ ኹሉ ዕንገት እያስደፋኝ
መንገዴ በሙሉ 0ጉኖ እያፋፋኝ ፣
ጠረጠርኩኝና ...
በኾነው በቀኑ መድረስኽን ረሳኹ ፤
በማወቅ ጉጉቴ . . .
ከመቅደስ ከፍታ ለመውደቅ ተነሣኹ።
( ፈተና ፫ )
ነባዊ . . .
ልባዊ . .
ሕያዊ . . .
መገመት ጀመሩ ፤ አንሰው ኮሰሱና
እሩጫው ዐየለ ፤ መስገድ እረሱና ፣
ሙዳይ መስፈራዬ አስገምቶኝ ከ'ኔ
ገዛኹ ፣ተገዛኹኝ ፤ በምድራዊው ቅኔ።
እናም . .
ልቤ ቃልን ስቶ
ለሥጋ ተገዝቶ
በዓለም ተመርቶ።
በሰው መኾን ግብር
አልችል ካለች ነፍሴ ፈተናውን ማለፍ፤
ይግባኝ ባሉት ብሂል ይቺ ጽዋ ትለፍ።
🔘ተስፋሁን ከበደ🔘
#ለኀጥአን_የመጣ
#ክፍል_አስራ_ሰባት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
“ደህና ነህ?” ብየ ጠየቅኩት::
ደህና ነኝ ብሎ ራሱን እያሻሸ ይቅርታ ይሄን ነገር እንደገና ስላነሳሁት እንደሚያስከፋህ ይገባኛል ግን እውነቱን መናገር አለብኝ” አለ። ክፍሉን እየዞረ የቅርብ ቤተሰቦችህን ማግኘት አልቻልንም። ስለዚህ አሳዳጊ ቤተሰብ ልንፈልግልህ ነው።
እንደሚስማማህ ተስፋ አለኝ፡፡ ሌላ ሃሳብ አለህ?”
“አዎ!” ብየ አባቴ ከጦርነቱ በፊት በዚህ ከተማ የሚኖር አንድ አጎት እንዳለኝ ይነግረኝ እንደነበር ነገርኩት።
ስሙ ማን ነው?”
“ቶሚ ይባላል እና አባቴ አናፂ እንደሆነ ነግሮኝ ነበር” ብየ መለስኩ።
“ምንም ቃል አልገባልህም፤ ግን የቻልኩትን እሞክራለሁ።በቅርብ እንገናኛለን” ብሎ ዝም ካለ በኋላ ትከሻየን እየነካካ “ ጥሩ እየሰራህ እንደሆነ ሰምቻለሁ። በርታ”አለኝ። ለስሊ በሰጠሁት ትንሽ መረጃ አጎቴን ከትልቅ ከተማ መሐል ያገኘዋል ብየ ተስፋ
አልታጣኩበትም ነበር። ለስሊ ከሄደ በኋላ ወደ አስቴር ሄድኩ።ለአስቴር ከ ለስሊ ጋር ስለበረን ቆይታ እና አጎቴን ያገኘዋል ብየ
እንደማልጠብቅ ነገርኳት። “ አይታወቅም! ሊያገኘው ይችላል” ” አለች::
አንድ ቀን ቅዳሜ ከስዓት ይመስለኛል ከአስቴር እና መሐመድ ጋር እየተጫወትኩ እያለ ለስሊ እየሳቀ መጣ። ጉድፈቻ የሚወስደኝ ቤት አግንቶልኛል፤ ልቀላቀል ነው ብየ ገመትኩ። ከማህበረሰቡ ጋር “መቀላቀል” ይሉታል ታዳጊ ወታደር የነበሩ ልጆችን ከ ዘመዶቻቸው ወይም ከአሳዳጊዎች ጋር ሲያገናኙ።
“ምንድን ነው መልካሙ ዜና?”ለስሊ ዜናውን ለመስማት ፤ጉጉቴን ፊቴን ላይ እያነበበ ወደ በሩ ተመልሶ በሩን ከፈተው።
አንድ ረጂም ሰውየ ገባ፡፡ ከአባቴ ትንሽ ጠቆር ያለ ፈገግታው ግን ደመቅ ያለ ሰው ነበር።
“አጎትህ ነው አለ ለስሊ በኩራት።
' እንዴት ነህ ልጄ እስማየል? አለ ሰውየው:: ጎንበስ ብሎ በረጅም እጆቹ ጠበቅ አርጎ አቀፈኝ፡፡ ምን አልባት እያስመስለ ቢሆንስ ብየ አሰብኩ። ለቆኝ አለቀሰ። ሲያለቅስ እውነትም ዘመዴ
እንደሆነ አመንኩ፡፡ ምክንያቱም የእውነት ነበር ያነባው፤ በሃገራችን ባህል ወንዶች እምብዛም አያለቅሱም::
“ይህን ሁሉ ጊዜ መጥቼ ስላላየሁህ ይቅርታ አድርግልኝ:: ከዝች ቀን በፊት መጥቼ አይቼህ ቢሆን ንሮ እንዴት ደስ ይለኝ ነበር። አሁን ያለፈው አልፏል። ዛሬ መጀመር እንችላለን። ስለ አጣሃቸው ቤተሰቦችህ በጣም አዝኛለሁ መፅናናተትን እመኝልሃለሁ። በርታ። ለስሊ ሁሉንም ነግሮኛል።” ለስሊን በአክብሮት አይን እየተመለከተ ቀጠለ “ ከዚህ ጨርሰህ ስትወጣ ከእኔ ጋር መጥተህ መኖር ትችላለህ። ልጄ ነህ! ብዙ የለኝም ግን የምታድርበት ቦታ፣ምግብ እና ፍቅር እስጥሃለሁ።” አለ።
ተነስቼ አጎቴን አቀፍኩት፤ እሱም አቅፎ ግንባሬን ሳመኝ፡፡ትንሽ ዝም ብለን ከቆየን በኋላ “ብዙ መቆየት አልችልም ከከተማ
ውጭ የጀመርኩት ስራ አለ። ለጊዜው ቅዳሜ እና እሁድ እየመጣሁ እጠይቅሃለሁ። አንተም ስትችል አንድ ቀን መጥተህ ቤቴን ታያልኛለህ:: ልጆቼን እና ባለቤቴን ቤተሰቦችህን ትተዋወቃለህ” አለ፡፡
“ጋሼ ከዚህ በኋላ ስለዚህ ልጅ ደህንነት እነግርዎታለን” አለ ለስሊ።
አመሰግናለሁ” አለ አጎቴ።
አጎቴ ስንሸኘው አባትህን ነው የምትመስለው ፤አስተዳደጋችንን አስታወስከኝ። እንደ አባትህ አስቸጋሪ
እንደማትሆን ግን ተስፋ አለኝ” አለ እየሳቀ። እኔም ሳቅኩ።
ስንመለስ አስቴር የቦብ ማርሌን ሙዚቃ ከፈተች እና አብረን ማዜም ጀመርን። “Three Little Birds” ሶስት ትናንሽ ወፎች “Dont Woy about a thing” ስለ ምንም ነገር አትጨነቅ
"Cause every little thing gonna be all right...."
ምክንያቱም ሁሉም መልካም ይሆናል
አጎቴን ስለማግኘቴ ለ አል ሃጂ እና ማቡ ልነግራቸው ፈለኩ ግን እነሱ ቤተሰብ ስላላገኙ ተሰማኝ።
አጎቴ ቃሉን ጠብቆ ቅዳሜ እና እሁድ እየመጣ ይጠይቀኝ ጀመር። ስጦታ ያመጣልኛል፣ ስለ አስተዳደጉ ይነግረኛል ስለ አባቴም ይጠይቀኝ ነበር። አንዴ አባቴ ስለነገረኝ አንድ የልጅነት ትውስታቸው ነገርኩት። አባቴ እና አጎቴ ውሃ ለመቅዳት ወደ ወንዝ ሲወርዱ ድንገት የንብ ቀፎ ያንቀሳቅሱ እና ንቦቹ ይከተሏቸዋል። አባቴ አጭር ስለነበር አብዛኛው ንብ ከአጎቴ ራስ
ላይ ነበር፡፡ ሩጠው ወንዝ ውስጥ ቢገቡም ጠብቆ ሊለቃቸው አልቻለም:: ስለዚህ ከውሃው ወጥተው ወደ መንደር ሲሮጡ ንቦቹን ወደ ሰፈር ይዘዋቸው መጡ።
“አዎ አስታውሳለሁ፡፡ ሁሉም ሰው ንቦቹን ወደ መንደር ይዘናቸው ስለመጣን አዝኖብን ነበር። መሮጥ የማችሉትን
ሽማግሌ ሰዎች እና ትንንሽ ህፃናትን ንቡ ነድፏቸው ነበር።አባትህ እና እኔ ግን በር ዘግተን አልጋ ስር ተደብቀን በሰዉ
እንስቅ ነበር” ብሎ ሲስቅ አብሬው ሳቅኩ፡፡
አንድ ቀን አጎቴ ቤተሰቦቹን ሊያስተዋውቀኝ ወደ ቤቱ ወሰደኝ::
ፍንትው ያለ ፀሐያማ ቅዳሜ ነበር። ኒው ኢንግላንድ ቬል New England Vile ውስጥ ነው የሚኖረው፡ውብ ከተማ ነበር። ቤቱግን መብራት ሆነ የቦንቧ ውሃ የለም። ወደ ደጁ ስንጠጋ የአጎቴ
ባለቤት ወጣች:: ፊቷ ያበራ ነበር፡፡ አጥብቃ አቀፈችኝ፡፡ ለቀቀችኝ እና ካየችኝ በኋላ ጉንጨን ቆንጥጣ “ እንኳን ደህና መጣህ ልጅ አለች:: አጠር ያለች ጥቁር ፣ ክብ ፊት እና አይኖቿ ጎላ ጎላ ያሉ ሴትዮ ነበረች። አባቴ የራሱ ልጆች አልነበሩትም ግን የቤተሰብ ልጆችን እንደራሱ አድርጎ ያሳድግ ነበር፡፡ አራት ነበሩ፦ አሌ
ትልቁ ሲሆን፣ ማቲልዳ፣ ኮና እና ሶሞ ይከተላሉ፡፡ የሚሰሩትን ስራ አቁመው መጥተው ሰላም አሉኝ፡፡ “ሌላ ወንድም ማግኘት ደስ ይላል” አለ አሌ እያቀፈኝ፡፡ ከተዋወቅን በኋላ ከአክስቴ እና ከአጎቴ በስተቀር ሁሉም ወደ ስራቸው ሄዱ። አክስቴ የምግብ አይነት እያመጣች ትደረድራለች፦ ሩዝ፣ አሳ፣ ሾርባ፣ አትክልት
ሌሎች ምግቦች። ሆዴ እስከሚነፋ ድረስ ብዙ በላሁ። ከምግብ በኋላ አጎቴ የአናፂ መሳሪያዎችን እና መስሪያ ቦታውን
አስጎበኘኝ፡፡
“ አናፂ መሆን የምትፈልግ ከሆነ ረዳቴ ልትሆን ትችላለህ። ግን እንደ አባትህ ትምህርት ቤት መግባት የምትፈልግ
ይመስለኛል” ሲል ፈገግ አልኩ። አሌ ተመልሶ መጣና አጎቴን ከእኔ ከእሱ ጋር ኳስ እንዲጫወት ፍቃድ ጠየቀ፡፡ አጎቴም እሱ ከፈለገ እሽ አለ፡፡ እኔ እና አሌ ተያይዘን ብሮክፊልድስ Brookfields ወደ ሚባል አካባቢ ሄድን።
“ወደ እኛ ስለመጣህ ደስ ብሎኛል:: የእኔን ክፍል መጋራት እንችላለን” አለኝ፡፡ በእድሜ ከእኔ ይበልጠኛል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱንም አጠናቋል። ደስተኛ ፣ ስርዓት ያለው እና ተናጋሪ ነው። ጨዋታው ከመጀመሩ በፊት አንዲት ቆንጆ ልጅ ወደ እኛ እጇን ታውለበልባለች። ማናት ብየ ከ መጠየቄ በፊት አሌ የአጎታችን ልጅ ናት ከመንገዱ ማዶ ከጉድ ፈቻ አሳዳጊዎቿ ጋር ነው የምትኖረው፡፡ አሚናታ ትባላለች ትተዋወቃላችሁ” አለኝ፡፡አሚናት የአባቴ ሁለተኛ ወንድም ልጅ ነች።
ኳስ ጨዋታውን እየተመለከትን የእኔ ልብ ግን የነበረው ይኖራል ብየ አስቤው የማላውቀው ቤተሰብ መገኘት ላይ ነበረ።
ደስተኛ ነበርኩ። ስንመለስ አጎቴ ወደ ማዕከሉ ሊመልሰኝ እየጠበቀኝ ነበር። እጄን ይዞ አውቶብስ ጣቢያው እስከምንደርስ ድረስ ምንም አላልኩም:: አውቶብስ ጣቢያው ስንደርስ ሌላ ጊዜ
በእራስህ ልትጎበኘን ከፈለክ ብሎ ገንዘብ ሰጠኝ፡፡
ከሁለት ሳምንት በፊት ለስሊ ወደ ማህበረሰቡ እንደምቀላቀል ነግሮኝ ነበር፡፡ ከአጎቴ ጋር ነው የምኖረው ሁለቱ
ሳምንቶች ቤኒን ቤት ካሳለፍኩት
#ክፍል_አስራ_ሰባት
#የታዳጊው_ወታደር_ትዝታ
#በኢስማኤል_ቤህ
#ክፍለእየሱስ_አበበ_እንደተረጎመው
“ደህና ነህ?” ብየ ጠየቅኩት::
ደህና ነኝ ብሎ ራሱን እያሻሸ ይቅርታ ይሄን ነገር እንደገና ስላነሳሁት እንደሚያስከፋህ ይገባኛል ግን እውነቱን መናገር አለብኝ” አለ። ክፍሉን እየዞረ የቅርብ ቤተሰቦችህን ማግኘት አልቻልንም። ስለዚህ አሳዳጊ ቤተሰብ ልንፈልግልህ ነው።
እንደሚስማማህ ተስፋ አለኝ፡፡ ሌላ ሃሳብ አለህ?”
“አዎ!” ብየ አባቴ ከጦርነቱ በፊት በዚህ ከተማ የሚኖር አንድ አጎት እንዳለኝ ይነግረኝ እንደነበር ነገርኩት።
ስሙ ማን ነው?”
“ቶሚ ይባላል እና አባቴ አናፂ እንደሆነ ነግሮኝ ነበር” ብየ መለስኩ።
“ምንም ቃል አልገባልህም፤ ግን የቻልኩትን እሞክራለሁ።በቅርብ እንገናኛለን” ብሎ ዝም ካለ በኋላ ትከሻየን እየነካካ “ ጥሩ እየሰራህ እንደሆነ ሰምቻለሁ። በርታ”አለኝ። ለስሊ በሰጠሁት ትንሽ መረጃ አጎቴን ከትልቅ ከተማ መሐል ያገኘዋል ብየ ተስፋ
አልታጣኩበትም ነበር። ለስሊ ከሄደ በኋላ ወደ አስቴር ሄድኩ።ለአስቴር ከ ለስሊ ጋር ስለበረን ቆይታ እና አጎቴን ያገኘዋል ብየ
እንደማልጠብቅ ነገርኳት። “ አይታወቅም! ሊያገኘው ይችላል” ” አለች::
አንድ ቀን ቅዳሜ ከስዓት ይመስለኛል ከአስቴር እና መሐመድ ጋር እየተጫወትኩ እያለ ለስሊ እየሳቀ መጣ። ጉድፈቻ የሚወስደኝ ቤት አግንቶልኛል፤ ልቀላቀል ነው ብየ ገመትኩ። ከማህበረሰቡ ጋር “መቀላቀል” ይሉታል ታዳጊ ወታደር የነበሩ ልጆችን ከ ዘመዶቻቸው ወይም ከአሳዳጊዎች ጋር ሲያገናኙ።
“ምንድን ነው መልካሙ ዜና?”ለስሊ ዜናውን ለመስማት ፤ጉጉቴን ፊቴን ላይ እያነበበ ወደ በሩ ተመልሶ በሩን ከፈተው።
አንድ ረጂም ሰውየ ገባ፡፡ ከአባቴ ትንሽ ጠቆር ያለ ፈገግታው ግን ደመቅ ያለ ሰው ነበር።
“አጎትህ ነው አለ ለስሊ በኩራት።
' እንዴት ነህ ልጄ እስማየል? አለ ሰውየው:: ጎንበስ ብሎ በረጅም እጆቹ ጠበቅ አርጎ አቀፈኝ፡፡ ምን አልባት እያስመስለ ቢሆንስ ብየ አሰብኩ። ለቆኝ አለቀሰ። ሲያለቅስ እውነትም ዘመዴ
እንደሆነ አመንኩ፡፡ ምክንያቱም የእውነት ነበር ያነባው፤ በሃገራችን ባህል ወንዶች እምብዛም አያለቅሱም::
“ይህን ሁሉ ጊዜ መጥቼ ስላላየሁህ ይቅርታ አድርግልኝ:: ከዝች ቀን በፊት መጥቼ አይቼህ ቢሆን ንሮ እንዴት ደስ ይለኝ ነበር። አሁን ያለፈው አልፏል። ዛሬ መጀመር እንችላለን። ስለ አጣሃቸው ቤተሰቦችህ በጣም አዝኛለሁ መፅናናተትን እመኝልሃለሁ። በርታ። ለስሊ ሁሉንም ነግሮኛል።” ለስሊን በአክብሮት አይን እየተመለከተ ቀጠለ “ ከዚህ ጨርሰህ ስትወጣ ከእኔ ጋር መጥተህ መኖር ትችላለህ። ልጄ ነህ! ብዙ የለኝም ግን የምታድርበት ቦታ፣ምግብ እና ፍቅር እስጥሃለሁ።” አለ።
ተነስቼ አጎቴን አቀፍኩት፤ እሱም አቅፎ ግንባሬን ሳመኝ፡፡ትንሽ ዝም ብለን ከቆየን በኋላ “ብዙ መቆየት አልችልም ከከተማ
ውጭ የጀመርኩት ስራ አለ። ለጊዜው ቅዳሜ እና እሁድ እየመጣሁ እጠይቅሃለሁ። አንተም ስትችል አንድ ቀን መጥተህ ቤቴን ታያልኛለህ:: ልጆቼን እና ባለቤቴን ቤተሰቦችህን ትተዋወቃለህ” አለ፡፡
“ጋሼ ከዚህ በኋላ ስለዚህ ልጅ ደህንነት እነግርዎታለን” አለ ለስሊ።
አመሰግናለሁ” አለ አጎቴ።
አጎቴ ስንሸኘው አባትህን ነው የምትመስለው ፤አስተዳደጋችንን አስታወስከኝ። እንደ አባትህ አስቸጋሪ
እንደማትሆን ግን ተስፋ አለኝ” አለ እየሳቀ። እኔም ሳቅኩ።
ስንመለስ አስቴር የቦብ ማርሌን ሙዚቃ ከፈተች እና አብረን ማዜም ጀመርን። “Three Little Birds” ሶስት ትናንሽ ወፎች “Dont Woy about a thing” ስለ ምንም ነገር አትጨነቅ
"Cause every little thing gonna be all right...."
ምክንያቱም ሁሉም መልካም ይሆናል
አጎቴን ስለማግኘቴ ለ አል ሃጂ እና ማቡ ልነግራቸው ፈለኩ ግን እነሱ ቤተሰብ ስላላገኙ ተሰማኝ።
አጎቴ ቃሉን ጠብቆ ቅዳሜ እና እሁድ እየመጣ ይጠይቀኝ ጀመር። ስጦታ ያመጣልኛል፣ ስለ አስተዳደጉ ይነግረኛል ስለ አባቴም ይጠይቀኝ ነበር። አንዴ አባቴ ስለነገረኝ አንድ የልጅነት ትውስታቸው ነገርኩት። አባቴ እና አጎቴ ውሃ ለመቅዳት ወደ ወንዝ ሲወርዱ ድንገት የንብ ቀፎ ያንቀሳቅሱ እና ንቦቹ ይከተሏቸዋል። አባቴ አጭር ስለነበር አብዛኛው ንብ ከአጎቴ ራስ
ላይ ነበር፡፡ ሩጠው ወንዝ ውስጥ ቢገቡም ጠብቆ ሊለቃቸው አልቻለም:: ስለዚህ ከውሃው ወጥተው ወደ መንደር ሲሮጡ ንቦቹን ወደ ሰፈር ይዘዋቸው መጡ።
“አዎ አስታውሳለሁ፡፡ ሁሉም ሰው ንቦቹን ወደ መንደር ይዘናቸው ስለመጣን አዝኖብን ነበር። መሮጥ የማችሉትን
ሽማግሌ ሰዎች እና ትንንሽ ህፃናትን ንቡ ነድፏቸው ነበር።አባትህ እና እኔ ግን በር ዘግተን አልጋ ስር ተደብቀን በሰዉ
እንስቅ ነበር” ብሎ ሲስቅ አብሬው ሳቅኩ፡፡
አንድ ቀን አጎቴ ቤተሰቦቹን ሊያስተዋውቀኝ ወደ ቤቱ ወሰደኝ::
ፍንትው ያለ ፀሐያማ ቅዳሜ ነበር። ኒው ኢንግላንድ ቬል New England Vile ውስጥ ነው የሚኖረው፡ውብ ከተማ ነበር። ቤቱግን መብራት ሆነ የቦንቧ ውሃ የለም። ወደ ደጁ ስንጠጋ የአጎቴ
ባለቤት ወጣች:: ፊቷ ያበራ ነበር፡፡ አጥብቃ አቀፈችኝ፡፡ ለቀቀችኝ እና ካየችኝ በኋላ ጉንጨን ቆንጥጣ “ እንኳን ደህና መጣህ ልጅ አለች:: አጠር ያለች ጥቁር ፣ ክብ ፊት እና አይኖቿ ጎላ ጎላ ያሉ ሴትዮ ነበረች። አባቴ የራሱ ልጆች አልነበሩትም ግን የቤተሰብ ልጆችን እንደራሱ አድርጎ ያሳድግ ነበር፡፡ አራት ነበሩ፦ አሌ
ትልቁ ሲሆን፣ ማቲልዳ፣ ኮና እና ሶሞ ይከተላሉ፡፡ የሚሰሩትን ስራ አቁመው መጥተው ሰላም አሉኝ፡፡ “ሌላ ወንድም ማግኘት ደስ ይላል” አለ አሌ እያቀፈኝ፡፡ ከተዋወቅን በኋላ ከአክስቴ እና ከአጎቴ በስተቀር ሁሉም ወደ ስራቸው ሄዱ። አክስቴ የምግብ አይነት እያመጣች ትደረድራለች፦ ሩዝ፣ አሳ፣ ሾርባ፣ አትክልት
ሌሎች ምግቦች። ሆዴ እስከሚነፋ ድረስ ብዙ በላሁ። ከምግብ በኋላ አጎቴ የአናፂ መሳሪያዎችን እና መስሪያ ቦታውን
አስጎበኘኝ፡፡
“ አናፂ መሆን የምትፈልግ ከሆነ ረዳቴ ልትሆን ትችላለህ። ግን እንደ አባትህ ትምህርት ቤት መግባት የምትፈልግ
ይመስለኛል” ሲል ፈገግ አልኩ። አሌ ተመልሶ መጣና አጎቴን ከእኔ ከእሱ ጋር ኳስ እንዲጫወት ፍቃድ ጠየቀ፡፡ አጎቴም እሱ ከፈለገ እሽ አለ፡፡ እኔ እና አሌ ተያይዘን ብሮክፊልድስ Brookfields ወደ ሚባል አካባቢ ሄድን።
“ወደ እኛ ስለመጣህ ደስ ብሎኛል:: የእኔን ክፍል መጋራት እንችላለን” አለኝ፡፡ በእድሜ ከእኔ ይበልጠኛል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱንም አጠናቋል። ደስተኛ ፣ ስርዓት ያለው እና ተናጋሪ ነው። ጨዋታው ከመጀመሩ በፊት አንዲት ቆንጆ ልጅ ወደ እኛ እጇን ታውለበልባለች። ማናት ብየ ከ መጠየቄ በፊት አሌ የአጎታችን ልጅ ናት ከመንገዱ ማዶ ከጉድ ፈቻ አሳዳጊዎቿ ጋር ነው የምትኖረው፡፡ አሚናታ ትባላለች ትተዋወቃላችሁ” አለኝ፡፡አሚናት የአባቴ ሁለተኛ ወንድም ልጅ ነች።
ኳስ ጨዋታውን እየተመለከትን የእኔ ልብ ግን የነበረው ይኖራል ብየ አስቤው የማላውቀው ቤተሰብ መገኘት ላይ ነበረ።
ደስተኛ ነበርኩ። ስንመለስ አጎቴ ወደ ማዕከሉ ሊመልሰኝ እየጠበቀኝ ነበር። እጄን ይዞ አውቶብስ ጣቢያው እስከምንደርስ ድረስ ምንም አላልኩም:: አውቶብስ ጣቢያው ስንደርስ ሌላ ጊዜ
በእራስህ ልትጎበኘን ከፈለክ ብሎ ገንዘብ ሰጠኝ፡፡
ከሁለት ሳምንት በፊት ለስሊ ወደ ማህበረሰቡ እንደምቀላቀል ነግሮኝ ነበር፡፡ ከአጎቴ ጋር ነው የምኖረው ሁለቱ
ሳምንቶች ቤኒን ቤት ካሳለፍኩት